ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
😏😏😏😁😁😁😁 @gedlatnadersanat @gedlatnadersanat @gedlatnadersanat @gedlatnadersanat


500 ሚሊዮን ነፍስ ከሲኦል ማስመለጥ

« #ወወሐባ ኪዳነ ከመ ታውጽእ ነፍሳተ እምሲኦል ሠለስተ እልፈ ነፍሳተ በበዕለቱ»
ትርጉም " #ጌታም በየቀኑ ከሲኦል ሦስት ሺህ ነፍሳትን እንድታወጣ ሥልጣን ሰጣት ወይም ቃል ኪዳን ሰጣት»
📖/ ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘጥቅምት ቁ 61...

500 ሚሊዮን የኢትዮጵያን ህዝብ 5 እጥፍ ነው። ይህ ቁጥር ክርስቶስ ሰምራ ከኖረችበት #ከአጼ ገብረ መስቀል መንግስት ጀምሮ #ለ450 አመታት በቀን #3000 ነፍሳት #ከሲኦል እንድታወጣ #ቃል ኪዳን ተቀበለች ከተባለላት ጀምሮ የተሰላ ነው። መቼስ እሱዋ ካወጣቻቸው ቀድሞውኑ ለምን #ሲኦል #ወረዱ የሚለው አጠያያቂ ቢሆንም መጽሃፍ ቅዱስ የሚያስተምረን ሲኦል ይቅርታ የሌለበት ያጠፉ የሚቀጡበት እንጂ በቃልኪዳን ስም እየተጨለፈ የሚወጣበት አይደለም።
እንዲህ አይነቱ ሰይጣን ሰዎች #ሲኦል ብወርድም #ክርስቶስ ሰምራ ታወጣኛለች ብለው፤ እንዲሁም " #ምንም እንደምድር አሽዋ ቢበዛ ሀጥአቴ፣ ታማልደኛለች #ድንግል እመቤቴ" እያሉ #በሃጢአታቸውና #በዝሙታቸው #በግድያቸው #በስርቆታቸው #እንዲገፉበትና #እንዳይጸጸቱ የሚሰራበት ሽንገላ ነው።

#ክርስቶስ ሰምራ #ባለትዳርና የ 11 ልጆች እናት ነበረች፤ ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት ባሪያዋ አበሳጨቻትና በእሳት ትንታግ ጉሮሮዋን #ጠብሳ #ገደለቻት ከዚያም #ተጸጽታ #ትዳሩዋንና #ልጆቹዋን #በትና ደብረ ሊባኖስ ገባች።

1= በዚህም እግዚአብሄር #ጋብቻ ቅዱስ ነው ያለውን ተላልፋ #መለያየትን እጠላለሁ ያለውን አልሰማም ብላ ራስ የሆነውን ባሉዋን አልሰማ ብላ፤ እግዚአብሄር በረከት ያላቸውን ልጆች #መንከባከብ #ትታ ጥላ በመጥፋት በድላለች/መጥፎ #ክርስቲያናዊ ያልሆነ #ምሳሌ ሆናለች።

2= (ወደ ጣና ሄዳ በጣና #ባሕር ውስጥ #ለ12 ዓመት ያህል ሳትነቃነቅ #ጸልያለች። በዚህ ጊዜ ሰውነቷ #አልቆ #አጥንት ብቻ #ቀርቷት ነበር። #አሳዎችም #ባጥንቶቿ ውስጥ መመላሻ መንግድ ጎጆና #መዝናኛ #ሠርተው ነበር።)
ይህ #የሰው ባህሪ ያልሆነ #ሃሰተኛና #አደገኛ #ተረት ነው። ይህ የሰው ባህሪ አይደለም። ጌታ እንኩዋን #ተርቦአል/ተጠምቶአል/ #ደክሞአል ኤሌያስም ተርቦ ደክሞት ነበር -ሰውነት ተበሳስቶ መኖር አይቻልም።

3. ክርስቶስ ሰምራ #በዲያብሎስና #በክርስቶስ መካከል ያለውን ጠላትነት ዘንግታ ዲያብሎስን ለማስታረቅ ወደ ሲኦል ወርዳ #ከዲያብሎስ ጋር #ተነጋግራለች። ይህ #ለዲያቢሎስ ፍቅር እንጂ #የእግዚአብሄር ፍቅር አይደለም።
2ኛ ቆሮ 6:15 “ ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን #መስማማት አለው? “ ይላልና #መንፈሳዊ ሰው ከሆነች ይህንን እንዴት አታውቅም….

4. « #ጌታም ተናገራት እንዲህ አላት #በአራት ወር ውስጥ በየቀኑ የሚወርደውን #የዝናብ #ነጠብጣብ ያህል #ነፍሳትን #አሥራት ሰጥቸሻለሁ» ወገኖቼ የአራት ወር #ዝናብ ነጠብጣብ ማለት ከአለም ህዝብ በላይ ነው።
ክህደቱ የሚጀምረው ገና ከመጀመሪያው ነው። #አሥራት ማለት ከአስር አንድ ማለት ሲሆን እሱም ከሰው ወደ እግዚአብሔር እንጂ ከእግዚአሃብሄር ወደ ሰው አይደለም።
#አለምና መላው ደግሞ #የኢየሱስ ክርስቶስ እንጂ የአንድ ፍጡር #የክርስቶስ ሰምራ አይደለም።

ወገኔ ዮሐ 15፥22። «እኔ መጥቼ ባልነገርኋችሁስ #ኃጢአት ባልሆነባችሁም ነበር» ይላልና ዛሬ እንዲህ አይነት አጋንንታዊ ተረት የምትከተሉ ጌታ ያስጠነቅቃችሁዋል ወደጌታ ተመለሱ።

1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:7
ነገር ግን ለዚህ ዓለም #ከሚመችና የአሮጊቶችን #ሴቶች #ጨዋታ ከሚመስለው #ተረት #ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

@gedlatnadersanat @teeod


ሮሜ 8÷34

" #የሞተው÷ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው÷ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው÷ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡"

#ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ መልእክቱ ማስተላልፍ የፈለገው ‹‹ #እንግዲህ #በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን #ኵነኔ የለባቸውም›› የሚለውን ነው (ቊጥር 1)፡፡ ሐዋርያው በመቀጠል ‹‹ #በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው #የሕይወት መንፈስ ሕግ #ከኀጢአትና #ከሞት ሕግ ዐርነት›› ያወጣን መሆኑን ያበሥርና (ቊጥር 2) እንደ #ሥጋ ፈቃድ ሳይሆን እንደ #መንፈስ ፈቃድ መመላለስ እንደሚገባን ይመክራል፡፡ ምክንያቱንም ደግሞ ‹‹ስለ #ሥጋ ማሰብ #ሞት ነውና÷ ስለ #መንፈስ ማሰብ ግን #ሕይወትና #ሰላም ነው›› በሚል ያስቀምጣል (ቊጥር 6)፡፡ ስለዚህ እንደ #ሥጋ ፈቃድ ሳይሆን እንደ #መንፈስ ፈቃድ መመላለስ እንደሚገባ ካሰፈረ በኋላ ‹‹ #አባ #አባት ብለን የምንጮኽበትን #የልጅነት #መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና #ለፍርሀት #የባርነትን #መንፈስ አልተቀበላችሁምና›› ይላል (ቊጥር 15)፡፡ በመቀጠል ልጆች ከሆንን ደግሞ ወራሾች ነን ይልና ‹‹ #ዐብረንም ደግሞ እንድንከበር ዐብረን #መከራ ብንቀበል #ከክርስቶስ ጋር አብረን #ወራሾች ነን›› የሚል ሐሳብ ያቀርባል፡፡ ነገር ግን #መከራው #ልንወርሰው ካለው ክብር ጋር ሲመዛዘን ‹‹ምንም እንዳይደለ አስባለሁ››፡፡ ይህ ግን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት በሙሉ በመሆኑ ‹‹ #የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች #መገለጥ›› በመቃተት በተስፋ እየተጠባበቀ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በመቃተት ላይ ያለው ግን #ፍጥረት ብቻ ሳይሆን እኛም ጭምር መሆናችንን ያስቀምጥና ‹‹ #እንዲሁም ደግሞ #መንፈስ #ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት #እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና÷ ነገር ግን #መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት #ይማልድልናል›› ይላል፡፡ ምክንያቱንም ‹‹ #ልብንም የሚመረምረው #የመንፈስ ዐሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል÷ እንደ #እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ #ቅዱሳን #ይማልዳልና›› በማለት ያስቀምጣል፡፡ ከዚህ ቡኋላ ቀደም ሲል ያቀረበውን በዚህ ምድር የሚያገኘንን #መከራ መነሻ በማድረግ ‹‹ #እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ #አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ #ለበጎ #እንዲደረግ እናውቃለን›› በማለት ይጀምርና #እግዚአብሔር #አስቀድሞ እንደ #ወሰነን፣ እንደ #ጠራን#እንዳጸደቀን እና #እንዳከበረን አስፍሮ ‹‹ #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን #ይቃወመናል?›› የሚል ጥያቄ ያነሣል፡፡ እንግዲህ ከዚህ ሁሉ በኋላ ነው ‹‹ #እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው÷ #የሚኰንንስ ማን ነው?›› የሚለውን ጥያቄ በማንሣት #የኰናኙን ማንነት ለማሳየት ጥረት የሚያደርገው፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት #ኰናኙ
▶️ "የሞተ"
(ሞቱ አንድ ጊዜ ብቻ የሆነ ወደፊት የማይደገም በመሆኑ በኃላፊ ጊዜ ነው የተቀመጠው)፣

▶️ "ከሙታንም የተነሣ"
(ትንሣኤውም ቢሆን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣበት ጊዜ ብቻ የሆነ አንድ ክንውን ነውና የተነሣ አለው)፣

▶️ "በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ"
(በእግዚአብሔር ቀኝ መሆኑ ስለ ሰው ልጆች ሊታይ ነው(ዕብ 9፥24)፡፡ ይሄውም የምልጃ ሥራው አካል ነውና አሁንም ስለ እኛ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ፡፡ ስለዚህ ነው ሐዋርያው በእግዚአብሔር ቀኝ ነበረ ሳይሆን አለ ያለው)፣

▶️ "ስለ እኛ የሚማልድ" (የክርስቶስ ምልጃ ምንም እንኳ አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ በተሠራው ሥራ የተፈጸመ ስለ ሆነ የማይደጋገም ቢሆንም፣ ቀደም ሲል እንደ ተባለው አሁንም ስለ እኛ በመታየት ይቅርታን እንድናገኝ ያደርጋልና ሐዋርያው ስለ እኛ የሚማልድ በማለት አሁንም አማላጃችን መሆኑን ተናገረ።) በማለት ስለ እኛ #የሚማልድ መሆኑን በማሳየት በዚህ ምድር ላይ ያለውን #መከራ #ማሸነፍ የሚቻልበትን #ማበረታቻ ይሰጣል፡፡ ይህ ምንባብ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #የሚከሳቸው #ማን ነው? ለሚለው #ጥያቄ #ማንም የሚል ምላሽ የሚሰጥ ሲሆን ማንም #ሊከሳቸው የማይችልበት #ምክንያት ደግሞ ስለ #እነርሱ #ሞቶ የነበረ #ሞትን #ድል አድርጎ #የተነሣው እና #በአብ ቀኝ ሆኖ #የሚያማልድላቸው #ስላለ ነው በሚል ነው የሚያስቀምጠው፡፡ #ሐዋርያው ቀደም ሲል #በክርስቶስ #ኢየሱስ ላሉት #አሁን #ኵነኔ የለባቸውም ማለቱን ማስታወሱም #ጠቃሚ ነው (ቊጥር 1)።
@ ( #ጳውሎስ "ስለ እኛ የሚማልደው" በማለት እርሱም #በክርስቶስ ኢየሱስ #የምልጃ ስራ ተጠቃሚ መሆኑን ይናገራል። አንዳንዶች #ሐዋሪያው #ጳውሎስን ጨምሮ በርካታ ሰዎችን #በምልጃ ስራ ውስጥ አሰልፈው #የክርስቶስን የምልጃ ስራ ፊት ለፊት በመቃወም ላይ ናቸው። #ሐዋሪያው በዚህ ክፍል ላይ እርሱ #አማላጅ ስለመሆኑ ሳይሆን #ስለ ኢየሱስ #አማላጅነት እና እርሱም #በኢየሱስ #ምልጃ ተጠቃሚ ስለ መሆኑ ነው የሚያስተምረው። #መጽሀፉ እንደሚለው ደግሞ #ኢየሱስ የእኛ ብቻ ሳይሆን #የቅዱስ ጳውሎስም #አማላጅ ነው። ስለ ሌሎች #ያማልዳል የሚባለው #ጳውሎስ #በክርስቶስ ምልጃ ተጠቃሚ እንደሆነ የገለጸውን መመልከት ሁላችንም #አማላጅ #እርሱ ብቻ ወደ ሆነው ወደ #ክርስቶስ እንድንጠጋ ያበረታታል።)

#በመቀጠልም ስለ እኛ #ከሞተው#ሞትን ድል አድርጎ #ከተነሣው#በእግዚአብሔር ቀኝ ካለው እና #ስለ እኛ #ከሚያማልደው ‹‹ #ከክርስቶስ #ፍቅር ማን ይለየናል? #መከራ÷ ወይስ #ጭንቀት÷ ወይስ #ስደት÷ ወይስ #ራብ÷ ወይስ #ራቁትነት÷ ወይስ #ፍርሀት÷ ወይስ #ሰይፍ ነውን?›› ሲል ይጠይቃል፡፡ በእርግጥም ከዚህ #ጌታ ምንም የሚለየን የለም፡፡ ‹‹ #ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ #እንገደላለን÷ #እንደሚታረዱ #በጎች ተቈጠርን ተብሎ›› ተጽፏልና፡፡ ‹‹በዚህ ሁሉ ግን #በወደደን [በአማላጃችን] #በእርሱ #ከአሸናፊዎች እንበልጣለን፡፡ #ሞት ቢሆን÷ #ሕይወትም ቢሆን÷ #መላእክትም ቢሆኑ÷ #ግዛትም ቢሆን÷ #ያለውም ቢሆን÷ #የሚመጣውም ቢሆን÷ #ኀይላትም ቢሆኑ÷ #ከፍታም ቢሆን÷ #ዝቅታም ቢሆን÷ #ልዩ ፍጥረትም ቢሆን #በክርስቶስ ኢየሱስ #በጌታችን ካለ #ከእግዚአብሔር #ፍቅር ሊለየን #እንዳይችል ተረድቼአለሁ›› በማለት #ምዕራፉ ያበቃል፡፡ #በዚህ ምዕራፍ ውስጥ #አሁን #ኵነኔ #የለብንም በማለት የጀመረው #ሐዋርያው #ክርስቲያኖች ስለሚያጋጥማቸው ነገር #እየመከረና #እያበረታታ ሁሉን #በጽናት #ማሸነፍ እንዳለባቸው ሲናገር፣ ‹‹ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው÷ #የሚኰንንስ ማን ነው?›› ለሚሉት #ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ‹‹ #ስለ እኛ የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ›› መሆኑን ነገረን፡፡ ለዚህስ ሳይሆን ይቀራል #በአንድምታው ላይ ‹‹ #እሱ #ቢያጸድቅ ማን #ይኰንነናል፡፡ #ኢየሱስ ክርስቶስ #ሞተ #ከሙታንም #ተለይቶ #ተነሣ፡፡ #በአብ #ዕሪና(እኩል፣ መተካከል) #ይኖራል ስለ እኛ #ይከራከራል፡፡ #መከራከርስ የለም #ስለ እኛ #በዕለተ #ዐርብ #ባደረገው #ተልእኮ ፍጹም #ዋጋችንን #የምናገኝ ስለ ሆነ›› እንደ ሆነ የሰፈረው????
📖/፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሀፍ ንባቡና ትርጓሜው (አ.አ፣ ግንቦት 1988) ገጽ 70።
📖/፤ መሐሪ ትርፌ (ሊቀ ሊቃውንት)፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሀፍ ንባቡ ከነትርጓሜው (አ.አ፤ ጥቅምት 23 1948) ገጽ 100።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ስለዚህም ክፍሉን ስናየው እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? ብሎ ጠየቀ ።ምን ብሎ መለሰ? << #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው>>ብሎ ነው የመለሰው ።ይህ ማለት ከሳሹ ማነው? #እግዚአብሔር ነው ማለት አይደለም ።ምክንያቱም #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ራሱ #አይከሳቸውምና በተመሳሳይም << #የሚኮንንስ ማነው? >ብሎ ጠየቀ ምን ብሎ መለሰ? የሞተው ይልቁንም #ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር…
<< #እግዚአብሔር የመረጣቸውን #የሚከሳቸው ማነው? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር
ነው>> ሮሜ8:33 አለ።

< #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> አለ። #እግዚአብሔር #የሚያጸድቀው #እነማንን
ነው? አግዚአብሔር #የሚያጸድቀው እሱ #የመረጣቸውን ነው።
እሱ < #የጠራቸውን እነዚህን #አጸደቃቸው> ሮሜ8:30 እግዚአብሔር #የመረጣቸውን እሱ ራሱ #የሚያጸድቃቸው ከሆነ እንግዲህ በእነዚህ ምርጦች ላይ ክስ ማንሳት የሚችል
ማነው? #ማንም ሊኖር አይችልም
#እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማንም #ሊከሳቸው አይችልም ለምን? ምክንያቱም #እግዚአብሔር #አምላካችን
#የመረጣቸውን #ምርጦቹን #የሚያጸድቅ አምላክ ነውና።
#እርሱ የመረጣቸውን
#ያጸድቃል ።እርሱ መርጦ #ያጸደቃቸውን ማን #ይከሳቸዋል?
<የጠራቸውን እነዚህን አጸደቃቸው> ተብሎ ተጽፏል። እርሱ እንዲህ አድርጎ ያጸደቀውን ማን
#ሊከስ ይችላል? ማንም #ሊከሳቸው አይችልም ።
---
<< #የሚኮንንስ ማነው? #የሞተው ይልቁን ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር ቀኝ
ያለው ደግሞም ስለ እኛ #የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው >>
ከላይ እንዳየነው #ዮሐንስ አፈወርቅ እንደገለጸው
<< #እግዚአብሔር ዘውዱን
አቀዳጅቶናል ማን #ይኮንነናል? #ክርስቶስ ስለሞተልን ደግሞም ከዚህ በኋላ
#ስለሚማልድልን ማን #ይኮንነናል>> ባለበት አገላለጽ ስንመለከተው
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #ያጸድቃቸዋል ፣ታዲያ እርሱ መርጦ #ያጸደቃቸውን
#የሚከሳቸው ማነው? #የሚኮንናቸውስ ማነው? ማንም #ሊኮንናቸው አይችልም።
እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #የሚኮንናቸውስ ማነው? ማንም።
እግዚአብሔር #ምርጦቹን #የመረጣቸው በክርስቶስ ነው ።
<< #ቅዱስና #ነውር የሌለን #በፍቅር እንሆን ዘንድ #በክርስቶስ ኢየሱስ
#መረጠን>>ኤፌ1:4
-
ይላል።
ታዲያ እነዚህ የእግዚአብሔር ምርጦች #በክርስቶስ ናቸው።
#በክርስቶስ #ኢየሱስ ላሉት ደግሞ #ኩነኔ የለባቸዎም << #በክርስቶስ #ኢየሱስ #ላሉት አሁን #ኩነኔ የለባቸውም >>ሮሜ8:1
#በክርስቶስ #ኢየሱስ የሆኑት እነዚህ የእግዚአብሔር ምርጦች አሁን #ኩነኔ #የለባቸውም#ኩነኔ #የሌለባቸውን እነዚህን ምርጦች ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም
#ሊኮንናቸው አይችልም።
ለምን? ምክንያቱም ለእነርሱ ሲል #የሞተ አለ ፣ለእነርሱ
ሲል #ከሞት የተነሳ አለ ፣ለእነርሱ ሲል #በእግዚአብሔር ቀኝ #የተቀመጠ አለ
፣ ለእነርሱ ሲል #የሚማልድ #ሊቀ #ካህናት አለ እርሱም #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው።
የእግዚአብሔር ምርጦች #ከኩነኔ #ነጻ የመሆናቸው #ማረጋገጫ በክርስቶስ ሞት
#ትንሣኤ#እርገት እና #ምልጃ ነው ።
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም #አይኮንናቸውም
ምክንያቱም ለእነርሱ ሲል #የሞተ አለ እርሱም #ክርስቶስ ነው።
#ክርስቶስ #ለምርጦቹ ሲል በደላቸውን ተሸክሞ በእንጨት ላይ #ሞቷል#በበደላቸው
የሚመጣባቸው #ፍርድ እሱ #ተሸክሟል #ፍርዱም #በሞቱ ተፈጽሟል ፣ታዲያ
#ክርስቶስ #ኢየሱስ የሞተላቸውን እነዚህን ምርጦች ማነው #የሚኮንን?
ከእግዚአብሔር ጋር በክርስቶስ #ሞት #ታርቀዋል /ሮሜ5:8/
ታዲያ ማነው #የሚኮንናቸው? ስለእነርሱ #መሞት ብቻ አይደለም ይልቁንም ስለ እነርሱ #ከሞት #ተነሥቷል ፣ለምን #ከሞት ተነሣ? ።
< #እኛን #ስለማጽደቅ #ከሙታን #ተነሣ> /ሮሜ4:24/
ተብሏል።
#ከሞቱ በበለጠ #ትንሣኤው #ከኩነኔ #ለመዳናቸው ትልቅ ዋስትናቸው ነው። እነርሱን #ለማጽደቅ ከሞት #ተነስቷል #በትንሣኤውም #ጸድቀዋልበክርስቶስ
#ትንሣኤ #የጸደቁትን እነዚህን የእግዚአብሔር ምርጦች #ማን #ይኮንናቸዋል?
እነዚህ ምርጦች #ከእግዚአብሔር ጋር #በልጁ #በክርስቶስ #ሞት #ታርቀዋል
ይልቁንም #ከሞት #ተነስቶ ሕያው ሆኖ በመኖሩ በህይወቱ ደግሞ ይድናሉ ፦
< #ከእግዚአብሔር ጋር #በልጁ ሞት #ከታረቅን #ይልቁንም ከታረቅን በኋላ #በሕይወቱ #እንድናለን> /ሮሜ5:11/
#ክርስቶስ ባይነሳ ኖሮ #ጽድቃቸው አይረጋገጥም
ነበረ ኃጢአተኛ ሆነው ይቀሩ ነበር << #ክርስቶስ #ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት
እስከ አሁን ድረሰ #በኃጢአታችሁ #አላችሁ>> /1ኛቆሮ15:17/ #በክርስቶስ ትንሣኤ
ዘለለማዊ #ጽድቅ አግኝተዋል።
#እግዚአብሔር #በልጁ #ትንሣኤ #ያጸደቃቸውን
ምርጦቹን ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም። ስለዚህ #የክርስቶስ #ትንሣኤ #ከኩነኔ #የሚድኑበት ማረጋገጫቸው ሆኗልና የእግዚአብሔርን ምርጦች ማንም
#አይኮንናቸውም
#ይህም ብቻ አይደለም #ክርስቶስ ወደ #ሰማይ አርጎ
#በእግዚአብሔር ቀኝ መቀመጡም ታላቅ የደኅንነት #ማረጋገጫቸው ነው።
#ክርስቶስ ወደ ሰማይ የወጣው #የሰዎችን ሥጋ #እንደያዘ ነው።
<< #ወደላይ
#በወጣህ ጊዜ ምርኮን ማረክህ>> /ኤፌ4:7/ እንደተባለ ክርስቶስ #በኃጢአት #በሕግ
#በሞት #በሰይጣን እንዲሁም ከማንኛውም ጠላት ሥር የነበረውን #የሰውን ሥጋ
ከጠላት ማርኮ በድል አድራጊነት ይዞት #በሰማያዊ ሥፍራ #በቀኙ ሥጋችንን #ሲያስቀምጠው በእርሱ #በኩል ከሞት በላይ መሆናችን ማንም ዝቅ ሊያደርገው
#በማይችል ከፍታ ላይ #መሆናችን ሲታወቅ በእርግጥም በእንዲህ አይነት ከፍታ
#ከፍ ያደረጋቸውን የእግዚአብሔር ምርጦች ማንም #ሊኮንናቸው አይችልም።
<< #ከክርስቶስ ጋር አስነሳን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ #ስፍራ ከእርሱ ጋር
#አስቀመጠን >> /ኤፌ2:7/ለው
ያለውም ይህን ነው ።
#ስለ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት #ይታይላቸው ዘንድ
ወደ ሰማይ #ገብቷልና #ማንም #ይኮንናቸው ዘንድ አይችልም
/ዕብ9:24/

እግዚአብሔር መርጦ #ያጸደቀንን ማን #ይከሰናል? #ክርስቶስ #ለኃጢአታችን
#የሞተልንን ማን #ይኮንነናል? #ክርስቶስ እኛን #ለማጽደቅ ከሞት ተነስቷል ታዲያ
ማን #ይኮንነናል? ስለ እኛ በእግዚአብሔር ፊት #ይታይ ዘንድ ወደ ሰማይ
ገብቷልና ማን #ይኮንነናል? ክርስቶስ #ስለ እኛ #ይማልዳልና ማን ይኮንነናል?

አሜን ሃሌ ሉያ። ማንም

የክፍሉ ዓብይ ሀሳብ ይህ ነው። ይህንን ከተረዳን። ነገ ደግሞ ስለዚህ ጥቅስ የተነሱትንና የተባሉትን የተለያዩ ኑፋቄዎች እንመለከታለን።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ሮሜ 8÷34 " #የሞተው÷ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው÷ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው÷ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡" #ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ መልእክቱ ማስተላልፍ የፈለገው ‹‹ #እንግዲህ #በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን #ኵነኔ የለባቸውም›› የሚለውን ነው (ቊጥር 1)፡፡ ሐዋርያው በመቀጠል ‹‹ #በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው #የሕይወት መንፈስ ሕግ #ከኀጢአትና…


1ኛ ጢሞቲዎስ 2፥5

"አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም #መካከል ያለው #መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም #ሰው #የሆነ #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው፤"

#የክርስቶስ ሰው የመሆን ምክንያት በዚህ መልእክት በሚገባ ሰፍሯል። በአዳም #በደል ምክንያት #ከእግዚአብሄር ፊት የራቀው #የአዳም ዘር ዳግመኛ #የእግዚአብሄርን #ፊት ለማየት የሚያስችል #ንጽህና ያልነበረው በመሆኑ፣ በእርሱ እና በአምላኩ #መካከል ያለውን #ክፍተት የሚሞላ ስላላገኘ፣ "አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን #አድን፤ አቤቱ፥ እባክህ፥ አሁን፥ #አቅና"፣ እጅህን፥ ከአርያም ላክ #አድነኝም" (መዝ 118፥25 ፣ 144፤ 7-8) በሚል በብዙ #ጩኸት ውስጥ ነበር። ክብር ለእርሱ ይሁንና ፍጹም #ሰው ፍጹም #አምላክ በሆነው #በክርስቶስ <<.... #በደሙ የተደረገ #ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም #የበደላችን #ስርየት>> ነው (ኤፌሶን 1፥7)።
" #መካከለኛ እንዲሆን እግዚአብሔር #አንድያ #ልጁን ላከው... [ምክንያቱም ደግሞ <<ወንድም ወንድሙን #አያድንም ሰውም #አያድንም>> እንደሚል(መዝ 49፥7) መጽሀፍ፥ #ሰው(ፍጡርና የአዳም ልጅ) #መካከለኛ ሊሆን... እና #ሊያድን የማይችል ደካማ #ፍጡር ነውና። የሰው ልጅ ብቻም ሳይሆን <<ከሰማይ #መላእክት እንኳ ቢሆን ከምድርም ሰው መካከል አንድስ እንኳ #ለመካከለኝነቱ ብቁ ሆኖ #ሰውና #እግዚአብሔርን #ማስታረቅ የተቻለው አልተገኘም አይገኝምም። "ደም ሳይፈስም ስርየት የለም"(ዕብ9፥22)። #በሰውና #በእግዚአብሄር #መካከል የነበረውን #የጥል #ግድግዳ ለማፍረስ በመካከል የገባ፣ ሁለቱን #ያስታረቀ፣ ሰውን ከሰማያዊ ርስት የቀላቀለ #ጌታ #ኢየሱስ #ብቻ ነው>>።
📖/፤ ብርሃኑ አበጋዝ፤
^ክርስቶስ^ (2007) ገጽ 38።
#ክርስቶስ #የመካከለኛነት ሥራውን የሰራው በመከራ ሞቱ በመሆኑ ሁላችን #በእርሱ #በኩል ወደ #እግዚአብሔር #የመቅረብ መብት እንድናገኝ አስችሎናል ለዚህ ነው መጽሀፍ ቅዱስ "እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን #በዐዲስና #በሕያው #መንገድ ወደ ቅድስት #በኢየሱስ #ደም በመጋረጃው ማለት #በሥጋው #በኩል እንድንገባ ድፍረት..." እንዳለን የሚያስተምረው (ዕብ 10፤ 19-20)።
#የክርስቶስን #የመካከለኝነት ሥራ ለመቀበል የከበዳቸው ሰዎች ለዚህ ጥቅስ የሚሰጡት መከላከያ #ሐሳብ ቢያጡ ከምንባቡ ውስጥ <<ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ>> የሚለውን መዘው በማውጣት በእርግጥ #ክርስቶስ በዚህ ምድር ሳለ #የመካከለኝነት #ሥራ ሰርቶ ነበር አሁን ግን እንዲህ ያለ ነገር #በእርሱ ዘንድ #የለም የሚል #ሐሳብ ያቀርባሉ። ወገኖቻችን በዚህ ስፍራ ላይ #ሐዋሪያው #ጳውሎስ #ክርስቶስን ^ #ሰው^ ማለቱን አላስተዋሉም ይሆን?? አሁን በሰማያት የእኛን ሥጋ ሥጋው ያደረገ መካከለኛ (ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ) አለን። ለዛም እኮ ነው መጽሀፍቅዱስ፤
""ስለእኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ ሰማይ ገባ"(ዕብ 9፥24 ፣ 28)""
""ስለእኛ የሚማልደው(ሮሜ 8፥34)፤""
""ዘውትር ሊያማልድ...ብሎም በእርሱ በኩል የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል(ዕብ 7፥25)፤""
""እንዲሁም በሰማይ ባለችው መቅደስ አገልጋይ"(ዕብ 8፥2)""
""የአዲስ ኪዳን መካከለኛ(ዕብ 9፥15፣ 12፥24)፤""
""በሚሻል ተስፋ ቃል በተመሠረተ በሚሻል ኪዳን ደግሞ #መካከለኛ #እንደሚሆን በዚያ ልክ እጅግ የሚሻል አገልግሎት አግኝቶአል።""(ዕብ 8፥6)
""ዘላለማዊ ሊቀካህን""(ዕብ 2፥17፣ 3፥1፣ 4፥14፣ 6፥20፣ 7፥26፣ 8፥1)....ወ.ዘ.ተ የሚለው።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..
@gedlatnadersanat @teeod
▶️ መድኃኒት የሚለው ቃል #በመጽሐፍ #ቅዱስ ውስጥ ያለው #ቦታ እጅግ ከፍ ያለ ነው፤ #ዳዊት ስለዚህ ሲናገር <<እግዚአብሔር አምባዬ አለቴ #መድኃኒቴ ነው>>/2 ሳሙ 22፥2/ ብሏል። በኢሳያስ አንደበትም እግዚአብሔር ለእስራኤል ሲናገር <<እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር #መድኃኒትህ ነኝ... እኔ እግዚአብሔር ነኝ #ከእኔ #ሌላ #የሚያድን የለም>> /ኢሳ 43፥3 ፣11/ ብሏል። እንደዚሁም ነብዩ በሌላ ቦታ ሰዎች እግዚአብሔርን <<የእስራኤል አምላክ #መድኃኒት ሆይ...>> ብለው እንደሚጠሩት ይናገርና በዚያው ክፍል ደግሞ #እግዚአብሔርም ስለራሱ በነቢዩ አንደበት <<እናንተ ከአህዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ ተሰብስባችሁ ኑ፤ በአንድነትም ቅረቡ የተቀረጸውን የምስላቸውን እንጨት የሚሸከሙና ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም። ይናገሩ ይቅረቡም በአንድነትም ይማከሩ ከጥንት ይህን ያሳየ ከቀድሞስ የተናገረ ማነው? ያሳየሁም የተናገርሁም እኔ እግዚአብሔር አይደለሁምን? ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም እኔ ጻድቅ አምላክና #መድኃኒት ነኝ ይላል>>/ኢሳ 45፥15 ፣ 20፥21/። በሌሎች ነብያትም <<ከእኔም በቀር ሌላ አምላክና #መድኃኒት የለም>>/ሆሴ 14፥4/ እያለ እግዚአብሔር ያውጅ ነበር። #መድኃኒትነት የእርሱ #ብቻ ነበርና ምንም እንኳን #በብሉይ ኪዳን #ሰንበት#በዓለ ሰዊት፣ #በዓለ መጸለት፣ #በዓለ ፍሥሐ፣ #በዓለ ናእት /የቂጣ በዓል/፣ #ኢዮቤልዩ የሚባሉ ታላላቅ #በዓላት ቢኖሩም ከእነዚህ አንዳቸውም #መድኃኒት አልተባሉም። ከእርሱ #ከእግዚአብሔር ሌላ #መድኃኒት እንደሌለ የተገነዘቡ የዘመኑ ነብያትም <<አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ ማለትም ኃይልህን አንሣ መጥተህም #አድነን>>/መዝ 80፥2/ ይሉ ነበር እንጂ ሰንበትን #መድኃኒታችን ነሽ አላሏትም። በአዲስ ኪዳንም #ድንግል #ማርያም ጌታን በጸነሰች ጊዜ <<ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፤ መንፈሴም በአምላኬ #በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች የባርይቱን ውርደት ተመልክቷልና>>/ሉቃ 1፥47/ብላለች። ጊዜው ደርሶ ጌታ #በተወለደ ሰዓትም #መላእክት በለሊት መንጋ ለሚጠብቁ እረኞች << ዛሬ በዳዊት ከተማ #መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ #ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና ብለው አበሰሩ>>/ሉቃ 2፥11/። #መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመካከላቸው ሲመላለስ ሕይወት ሰጪ ትምህርቱን የሰሙት የሰማርያ ሰዎችም ስለእርሱ ሲናገሩ << እኛ ራሳችን ሰምተነዋልና፤ እርሱም በእውነት ክርስቶስ #የዓለም #መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለን>> ሲሉ ክርስቶስ መድኃኒት መሆኑን ተናግረዋል/ዩሀ 4፥42/። በእርግጥም #ጌታ እኛን ለማዳን #በመስቀል ላይ #ሞቶ ወደ ከርሠ መቃብር ወርዶ #ሞትን ድል ማድረግ ነበረበትና እንደ #መጻሕፍት ሐሳብ #በኃጢአተኞች እጅ ተሰጥቶ #ሞተ። እንደ እግዚአብሔር አሠራርም #ሞትን #አሸንፎ ተነሣ። ይህንን በዓይናቸው ያዩና የተገነዘቡ #ሐዋርያትም #ጌታ #ካረገ ቡኋላ ስለእርሱ #ለአይሁድ ሸንጎ ሲናገሩ <<እናንተ በእንጨት ላይ ሰቅላችሁ የገደላችሁትን ኢየሱስን የአባቶቻችን አምላክ አስነሣው፤ ይህን እግዚአብሔር፥ ለእስራኤል ንስሐን የኃጢአትንም ስርየት ይሰጥ ዘንድ፥ #ራስም #መድኃኒትም አድርጎ በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው>> ሲሉ ራስና #መድኃኒት ስለመሆኑ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል/ሐዋ 5፥31/። ኢየሱስ ማለት #አዳኝ #መድኃኒት ማለት ነው፤ #ዕለተ #ሰንበት ማዳን ብትችል ኖሮ "ወልደ እግዚአብሔር" #ሰው መሆን ባላስፈለገው ነበር።
#የሐዲስ ኪዳን #ምእመናን #ለመዳን እጆቻቸውን ወደማንም አያነሡም፤ #መዳን #በክርስቶስ ካልሆነ #በቀር በሌላ #በማንም... የለምና/ሐዋ 4፥12/። #እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን የሚያስችለውን #ከክርስቶስ ሌላ አማራጭ ቢፈልግ ኖሮ #ከሰንበት ይልቅ ብዙ ታላላቅ #ፍጥረታት ነበሩት፤ ሆኖም ግን #ከፍጥረት ወገን #ለማዳን የሚበቃ አልነበረምና #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ብቻውን #ለሰው ልጆች #መድኃኒት ሆነ።
እንደዚሁም በዚህ መጽሀፍ #ሰንበት <<ለዘላለም ገዥ>> ተብላለች፤ #በመጽሀፍ #ቅዱስ ስንመለከት ግን #ሰንበት ለሰው #ተፈጠረች እንጂ ሰው #ስለሰንበት #አልተፈጠረም። ሰዎችንም #ልትገዛ ከቶ አትችልም፤ #ለዘላለም የመኖር እድልም የላትም፤ የእርሷ #የጥላነት ጊዜ አብቅቶ #አካሉ #ክርስቶስ ተገልጧልና።

▶️ መድኃኒትነትም ሆነ #ገዥነት ያለው እርሱ #እግዚአብሔር #ብቻ ነው። መጽሀፍ ቅዱስ <<ብቻውን የሆነ ገዢ>> የሚለው እርሱን #ብቻ ነው/1ጢሞ 6፥15/። እንደዚሁም <<እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም፣ ወገበረ #መድኃኒት በማዕከለ ምድር ማለትም #እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው በምድርም መካከል #መድኃኒትን አደረገ>>/መዝ 74፥12/ የተባለለት የዘለዓለም ንጉሥ አንድ ጌታ ነው እንጂ ሰንበት አይደለችም።
እንደዙሁም ይች #ሰንበት <<ለምኝልን>> ተብላለች። አንዲት የማትሰማና #የጊዜ #መለኪያ ብቻ የሆነችው ^ዕለት^ #አፍ አውጥታ #እንድትናገርና በእግዚአብሄር ፊት ቆማ #እንድታማልድ ወደ እርሷ #እጅን #ዘርግቶ #መማጸን ወደ ልቡ ተመልሶ #ላስተዋለው ሰው ምን ያህል #አሳፋሪ መሆኑን መገንዘብ አያዳግትም። ቃሉ ግን እኛ ራሳችን #በኢየሱስ #ክርስቶስ #ስም #እግዚአብሔርን እንድለምነው ሲያስተምረን እንደዚህ ይለናል፤ <<ማናቸውንም ነገር #በስሜ #ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ>>/ዩሀ 14፥13/፤ <<የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል>>/ዩሀ 15፥7/፤ <<እውነት እውነት እላቹሀለው #አብ #በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችሀል እስከ አሁን #በስሜ ምንም አለመናችሁም ደስታችሁ ፍጹም እንዲሆን ለምኑ ትቀበሉማላችሁ>>/ዩሀ 16፤ 23-24/።
በዚህ መሰረት ወደ ማን #መለመን እንዳለብን ግልጽ ነው፤ በአጠቃላይ #ጸሎታችንና #ልመናችን #በኢየሱስ #በኩል ወደ #አብ እንዲደርስ እንጂ #በሌላ #በኩል ማለትም #በሰንበት ወደ #አብ መግባት እንደማይችል ልንረዳ ይገባል። ጌታም <<በእኔ #በቀር ወደ #አብ የሚመጣ #የለም>> ማለቱ ለዚሁ አይደለምን/ዩሀ 14፥6/?

@gedlatnadersanat
<<እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ...>> የሚለውን የተቀነባበረ <የጸሎት> ክፍል #በኢየሱስ ክርስቶስ #አስተምህሮ #ወቅት ብቻ ሳይሆን ከእሱ ቡሀላም ለብዙ #ዘመናት አልነበረም። ምናልባትም ሌሎች እንደሚሉት #ማርያም ገና #ክርስቶስን ሳትወልድ የነበረ #የገብርኤል #ሰላምታ ነው ተብሎ እንዳይወሰድ እንኳን #መልአኩ መጥቶ ያደረገው #ውይይት እንጂ #ጸሎት አይደለም። #ክርስቶስም #ለደቀመዛሙርቱ #ጸሎት ባስተማረበት #ወቅት #የገብርኤልንም #ሰላምታ ጨምሩበት በማለት ባስተላለፈ ነበር፤ ያንን ደግሞ አላደረገውም [ማቴ 6፤ 1-13፣ ሉቃ 11፤ 1-4]። << #በሰማያት የምትኖር #አባታችን ሆይ....>> የሚለው #የጸሎት #አስተምህሮቱን #ድንግል ማርያምን በትክክል በሚያውቋት #በደቀመዛሙርቱ ፊት ምናልባትም #በአስተምሮው #ወቅት ብዙ ጊዜ በምትገኝዋም #በድንግል #ማርያምም በራሷ ፊትም ተናግሯል።

▶️ ስለሆነም የተቀነባበረው <<የማርያም የጸሎት>> ምዕራፍ #በክርስቶስ #ወቅት ያልነበረ ከዚያም ቡኋላ #ሐዋሪያቱ #በአገልግሎታቸውና #በጸሎታቸውም ወቅት የማያውቁትና #የጥንት #ቤተ ክርስቲያን #አባቶችም በልዩ ልዩ ምክንያት #ጉባኤ ሲያደርጉ ለምሳሌ፦ #በኒቂያ ጉባኤ #በ325 ዓ.ም 318 የሃይማኖት አባቶች በእነ #እስክንድሮስ አፈጉባዔነት በንጉስ #ቆስጠንጢኖስ ዘመን ተሰብስበው #አርዮስን <<ወልድ #ፍጡር ነው>> ያለበትን #የክህደት ትምህርት #ሲያወግዙና #የሃይማኖት መግለጫ ሲያወጡ #ኢየሱስን ከመውለዷ ውጭ #ስለማርያም ፈጽሞ #መሠረታዊ #ትምህርት እንኳ በወቅቱ እንዳልነበረ መረዳት ይችላል። እንዲሁም #በቁስጥንጥንያ #በ375 ዓ.ም 150 #የሃይማኖት #አባቶች #በጢሞቴዎስ ዘአልቦጥሪት በንጉሥ ዘየዓቢ #ቴዎደስዩስ ወቅት #መቅደንዩስ << #መንፈስ ቅዱስ #ሕጹጽ ወይም #ሀይል ብቻ>> ብሎ በተነሳ ጊዜ ተሰብስበው #አውግዘው ትምህርቱንና እርሱን ሲለዩ #የቤተክርስቲያንን አጠቃላይ #የአስተምህሮ #መግለጫ ሲያወጡ ያኔም ቢሆን #ኢየሱስን #ከመውለዷ ውጪ #ስለማርያም ያስተላለፉት ምንም #አዲስ #ትምህርት የለም። #በኤፌሶን ሀገርም #በ435 ዓ.ም 200 #የሃይማኖት #አባቶች #በቄርሎስ አፈጉባዔነት በቴዎደስዩስ ዘይንእስ ንጉሥነት ጊዜ ንስጥሮስ << #ክርስቶስ #ሁለት #አካል #ሁለት #ባህሪይ ነው>> ብሎ ሲነሳ #እርሱንም #ትምህርቱንም #አውግዘው #የቤተክርስቲያንን አጠቃላይ #አስተምህሮ በመግለጫ መልክ ሲያስቀምጡ ድንግል #ማርያም #ክርስቶስን እንደወለደች ብቻ እንጂ << #እመቤታችን>> ብለውም ሆነ << #ለምኝልን>> የሚል አስተምህሮ አያውቁም። #ጤናማ #አስተምህሮ አይደለምና።

▶️ ዛሬ ሁሉም #አብያተክርስቲያናት የሚቀበሉት #ሙሉ #የሃይማኖት #መግለጫቸው

<<ሁሉን በያዘ ሰማይና ምድርን የሚታይና የማይታየውን በፈጠረ በአንድ አምላክ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን። ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋር በነበረ የአብ አንድ ልጁ በሚሆን በአንድ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስም እናምናለን። ከብርሃን የተገኘ ብርሃን የተፈጠረ ሳይሆን የተወለደ በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል ሁሉ በእርሱ የሆነ ያለ እርሱ ግን ምን ምንም የሆነ የለም በሰማይም ያለ በምድርም ያለ ስለእኛ ስለ ሰዎች ስለመዳናችን ከሰማይ ወረደ ከቅድስት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር ፈጽሞ ሰው ሆኖ በጴንጤናዊ በጲላጦስ ዘመን ስለ እኛ ተሰቀለ ታመመ ሞተ ተቀበረም በሶስተኛውም ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሳ። በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ ዳግመኛም በሕያዋንና ሙታንንም ይፈርድ ዘንድ በጌትነት ይመጣል ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም ጌታ ማህየዊ በሚሆን ከአብ በሰረጸ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋር በነብያት የተነገረ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋሪያት በሰበሰባት በአንዲት ቤተክርስቲያን እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተሰረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። የሙታንንም መነሳት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ አሜን።>> የሚል ነው።

ይህንንም መግለጫ #በ1530 ዓ.ም #ሉተራውያን << #የአውግስበርግ #መግለጫ>> በሚል አጸደቁ። እንዲሁም #በ1546 ዓ.ም #ካቶሊክ በድጋሜ << #የትሬንት #መግለጫ>> በማለት አጸደቀችው። #በ1571 ዓ.ም ደግሞ #የአንግሊካን #ቸርች መግለጫውን ተቀብላ አጸደቀችው። #በ1646 ዓ.ም #ፕሪስቢቴሪያን << #የዌስት #ሚኒስቴር #መግለጫ>> በሚል አጸደቀችው[1]።

▶️ ኦርቶዶክስ #ቤተክርስቲያን መግለጫውን በድጋሜ << #ጸሎተ #ሃይማኖት>> በማለት #በ1426-1460 ዓ.ም በኢትዮጵያ የነገሰው #አጼ #ዘርዓ ያዕቆብ ሙሉውን ተቀበሉና ሌላ #በመጨመር << #ለማርያምና #ለእፀ መስቀሉ (ለመስቀሉ እንጨት) #ስግደት ይገባቸዋል>> በማለት እንዲሁም <<እመቤታችን ...ሆይ>> የሚለውን <<ከአባታችን ሆይ>> #ቀጥሎ እንዲባል ብሎ #አዋጅ አወጣ። ከዚህም የተነሳ በርካታ #ካህናት << #አባቶቻችን ካስቀመጡት #ከሃይማኖት #መግለጫው ውጪ ተጨማሪውን #አንቀበልም>> በማለታቸው #በሰይፍ እንደቆራረጣቸውና እንዳሳደዳቸው #ገድለ #እስጢፋኖስ#ገድለ #አበው ወአኀው፣ #ገድለ #አባ አበከረዙል፣ #ገድለ #አባ ዕዝራ፣ #ገድለ #ደቂቀ እስጢፋኖስን ማንበብ #በቂ ነው።

▶️ ነገር ግን #በዘር #ቅብብሎሽ አማካኝነት የነበረው #የንግስና #ሥርአት ለዚህ <<አዳራሻውን ወደ ሳተው ጸሎት>> ሰፊ እድል አግኝቶ #ሰይፍ ያስፈራቸውና በክርስትናው #ትምህርት ብዙም #መሰረታዊ #እውቀት ያልነበራቸው #ህዝብና #ካህናት #የጸሎት #ምዕራፋቸው አድርገው ለቀጣዩ #ትውልድ በማስተላለፋቸው ይሀው አሁን የምናየውን #ከእግዚአብሄር #ቃል ውጪ የሆነ #ትውልድ ፈጥረውልናል። ዛሬ ዛሬ #በየጸሎቱ #መዛግብት ውስጥ እየተጨመረ ተጽፎ #ምዕመናን ሁሉ #በቀን ቢያንስ #አንድ ጊዜ እንዲደግመው በመደረጉ እንግዳው <<ጸሎት>> #የተለመደ ሆኖ ቀረ። እንዲያውም በዚህ #ዘመን አስቀድመን እንዳልነው <<እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ...>> የሚለውን #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ለማስመሰል #ጥቅሶችን ያለቦታቸው እንደ #ስጋ #ዘንጥለውና #በጣጥሰው #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ለማስመሰል የሚታገሉ ተነስተዋል። እኛ ግን <<የእግዚአብሔርን ቃል #ቀላቅለው #እንደሚሸቃቅጡት እንደ #ብዙዎቹ አይደለንምና፤ #በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ #ተላክን #በእግዚአብሔር ፊት #በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።>> [2ቆሮ 2፥17]

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን፤ አውግስበርግ ሃይማኖታዊ መግለጫ፤ በአማርኛ የተተረጎመ፤ አ.አ፥ 1993 ዓ.ም።
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ነብያት#ካህናት#ሐዋሪያት #ሁሉም ማለት ይቻላል ጸልየዋል። #ጸሎታቸውም በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር እንጂ እንኳን ወደ #ፍጡራን፣ ወደ #መላእክት የጸለየ አንድም #ሰው አናገኘም። #ድንግል #ማርያም እንኳን #በሉቃስ 1፤46-55 እንደተገለጸው <<ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፤ መንፈሴም በአምላኬ በመድሃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች.....>> በማለት እንዲሁም #በሐዋ 1፥25 #ከ120 #ሰዎች ጋር አብራ <<የሁሉንም ልብ የምታውቅ ጌታ ሆይ>> እያለች በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ነው የጸለየችው። #ኢየሱስ ክርስቶስም #በሥጋው ወራት #በርካታ ጊዜ ያለማቋረጥ ወደ #አባቱ <<አባት ሆይ...>> በማለት #ጸሎት አድርጓል [ዩሀ 17፥1]። #ክርስቶስ አገልግሎቱን #በጸሎት ጀምሮ [ማቴ 4፥1] በመስቀል ላይ #ነፍሱን ሲሰጥና #አገልግሎቱን ሲደመድም #በጸሎት ውስጥ ነበር። እርሱ እንዳደረገውም #እንዳስተማረን <<አባታችን ሆይ>> ብለን እንድንጸልይ እንጂ <<እመቤታችን ሆይ>> ብለንም ሆነ #ወደሌላ #እንድንጸልይ አላስተማረንም።

▶️ ክርስቶስ ስለ #ጸሎት ሁኔታ ከሰጠን #መመሪያዎች ውስጥ <<አንተ ግን ስትጸልይ ወደ እልፍኝ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሀል>> [ማቴ 6፥6] ብሎ ነው ያዘዘን። #ሐዋሪያትም ቢሆኑ #ከክርስቶስ የተማሩትን #ትምህርት #አብነት (ምሳሌ) አድርገው <<የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ...">> [ #ሐዋ 1፥25]፣ <<ጌታ ሆይ አንተ ሰማዩንና ምድሩን ባሕሩንም በእርሱም የሚኖረውን ሁሉ የፈጠረህ...>> [ #ሐዋ 4፥24] ፣<<ጌታ ኢየሱስ ሆይ...>> [ #ሐዋ 7፥59]..ወ.ዘ.ተ በማለት #ቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ብቻ ነው የጸለዩት። ስለሆነም እንደ እነርሱ #መጽሀፍቅዱስ <<በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ>> በሚለው መመሪያ መሰረት [ #ፊል 4፥6] ወደ #እግዚአብሔር #ቀጥታ እንድንጸልይ ያሳስበናል።

▶️ ጸሎት በራሱ #የቃሉ #ትርጉም #ከእግዚአብሄር ጋር #መነጋገር ማለት እግዚአብሔርን #ማክበር [ራዕ 4፤ 10-11] እግዚአብሔርን #ማመስገን [መዝ 106(107) ፤1-2] እግዚአብሔርን #መለመን [ያዕ 1፤5] እግዚአብሔር የሚናገረውን #ማዳመጥ [መዝ 84(85) ፤8] ማለት ነው። ለዛም ነው ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ ያለው <<ሥጋ ለባሽ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል።>> ያለው [ #መዝ 65፥2]። በዚህም መሰረት በብሉይ ኪዳን #አዳም#ኖህ#አብርሃም#ይስሐቅ#ያዕቆብ#ዮሴፍ#ሙሴ#ኢያሱ#የሳሙኤል እናት #ሐና#ሳሙኤል#ጌድዮን#ባርቅ#ሳምሶን#ዮፍታሔ#ዳዊት#ሰለሞን#ኤልያስ#ኤልሳዕ#ኢዮስያስ#ሕዝቅያስ#ኢሳይያስ#ኤርምያስ#ኢዮብ#ዕዝራ#ነህምያ#አስቴር#ዳንኤል#ሕዝቅኤል#ዮናስ . . .ወዘተ በሐዲስ ኪዳንም 12ቱ #ደቀመዛሙርት#ድንግል ማርያም፣ #ዘካርያስ#ስምዖን#ጳውሎስ#ጴጥሮስ፣ በህብረት ደግሞ #ጳውሎስና #ሲላስ#ሐዋርያት #በአንድነት፣ ራሱም #ኢየሱስ ክርስቶስ #በሥጋዌ ማንነቱ፣ እጅግ #ኃጢአተኞች ተብለው የሚቆጠሩት #በክርስቶስ ቀኝ የተሰቀለው #ወንበዴና ከሰፈር ውጭ ተጥለው የነበሩት #ለምጻሞች ሁሉ #ጸልየዋል። የጸለዩትም #ጸሎት #በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ሆኖ የከበረ #መልስ ማግኘታቸውም ሁሉ ለትምህርታችን #ተጽፏል። ስለዚህ ወደ #ማርያምም ሆነ ወደ ማንኛውም #ፍጡር መጸለይ #ኢ #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ዘመን አመጣሽ #ተግባር ነው። ደግሞም ዛሬ በአንዳንድ #ምእመናን እንደሚታየው ከላይ የጠቀስናቸው ሁሉ #ለመጸለይ #የልባቸውን #ጩኸት አቀረቡ እንጂ #ለጸሎት ብለው የተጠቀሙበት #የጸሎት #መጽሐፍ <<የሰኞ የማክሰኞ>> ወ.ዘ.ተ እያሉ የሚደግሙት #መጽሐፍ አልነበራቸውም። #በብሉይ ኪዳን ተጽፎ የነበረው #የመዝሙረ ዳዊት #መጽሐፍ #ኢየሱስ ክርስቶስና #ሐዋርያት ለትምህርቶቻቸው ይጠቅሱት ነበር እንጂ #ለጸሎቶቻቸው #ድጋፍ አድርገው አልተጠቀሙበትም። ስለዚህ #ጸሎት #ከልብ የሚመነጭ ስለሆነ በየቀኑ በብዙ #ገጾች የሚቆጠሩ የተለያዩ #ርዝመት ያላቸውን የተጻፉ #መጽሀፍትን #ማዘጋጀትና#መደጋገም እንዲሁም #ህመም ሲሰማቸው #መጽሀፍቶቹን #መተሻሽት#በራስጌ ላይ #ማንጠልጠል#በአንገት ላይ #ማነገት አይደለም።

▶️ ጌታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን #የፈሪሳውያን (የአህዛብ) #ጸሎት #ስነ - ሥርዓት <<አህዛብም በመናገራቸው #ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና #ስትጸልዩ እንደ እነርሱ #በከንቱ አትድገሙ ስለዚህ አትምሰሏቸው>> በማለት ተቃውሟል [ማቴ 6፤ 7-8]። ስለዚህ #ጸሎት ሰዎች በደረሱልን የ"ጸሎት" #ድርሰት #መጽሀፍ ወይም የሌሎችን #ጸሎት በመድገም #መጸለይ ሳይሆን እንደ ጌታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ #እግዚአብሔር በመቅረብ የልባችንን #ጸሎት #በእውነትና #በመንፈስ #ከአክብሮት ጋር በማቅረብ ነው [ማቴ 26፤ 39-44 ፣ ዩሀ 17፤ 1-26]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆