ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ስለዚህም ክፍሉን ስናየው እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? ብሎ ጠየቀ ።ምን ብሎ መለሰ? << #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው>>ብሎ ነው የመለሰው ።ይህ ማለት ከሳሹ ማነው? #እግዚአብሔር ነው ማለት አይደለም ።ምክንያቱም #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ራሱ #አይከሳቸውምና በተመሳሳይም << #የሚኮንንስ ማነው? >ብሎ ጠየቀ ምን ብሎ መለሰ? የሞተው ይልቁንም #ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር…
<< #እግዚአብሔር የመረጣቸውን #የሚከሳቸው ማነው? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር
ነው>> ሮሜ8:33 አለ።

< #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው>> አለ። #እግዚአብሔር #የሚያጸድቀው #እነማንን
ነው? አግዚአብሔር #የሚያጸድቀው እሱ #የመረጣቸውን ነው።
እሱ < #የጠራቸውን እነዚህን #አጸደቃቸው> ሮሜ8:30 እግዚአብሔር #የመረጣቸውን እሱ ራሱ #የሚያጸድቃቸው ከሆነ እንግዲህ በእነዚህ ምርጦች ላይ ክስ ማንሳት የሚችል
ማነው? #ማንም ሊኖር አይችልም
#እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማንም #ሊከሳቸው አይችልም ለምን? ምክንያቱም #እግዚአብሔር #አምላካችን
#የመረጣቸውን #ምርጦቹን #የሚያጸድቅ አምላክ ነውና።
#እርሱ የመረጣቸውን
#ያጸድቃል ።እርሱ መርጦ #ያጸደቃቸውን ማን #ይከሳቸዋል?
<የጠራቸውን እነዚህን አጸደቃቸው> ተብሎ ተጽፏል። እርሱ እንዲህ አድርጎ ያጸደቀውን ማን
#ሊከስ ይችላል? ማንም #ሊከሳቸው አይችልም ።
---
<< #የሚኮንንስ ማነው? #የሞተው ይልቁን ከሙታን የተነሣው #በእግዚአብሔር ቀኝ
ያለው ደግሞም ስለ እኛ #የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው >>
ከላይ እንዳየነው #ዮሐንስ አፈወርቅ እንደገለጸው
<< #እግዚአብሔር ዘውዱን
አቀዳጅቶናል ማን #ይኮንነናል? #ክርስቶስ ስለሞተልን ደግሞም ከዚህ በኋላ
#ስለሚማልድልን ማን #ይኮንነናል>> ባለበት አገላለጽ ስንመለከተው
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #ያጸድቃቸዋል ፣ታዲያ እርሱ መርጦ #ያጸደቃቸውን
#የሚከሳቸው ማነው? #የሚኮንናቸውስ ማነው? ማንም #ሊኮንናቸው አይችልም።
እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #የሚኮንናቸውስ ማነው? ማንም።
እግዚአብሔር #ምርጦቹን #የመረጣቸው በክርስቶስ ነው ።
<< #ቅዱስና #ነውር የሌለን #በፍቅር እንሆን ዘንድ #በክርስቶስ ኢየሱስ
#መረጠን>>ኤፌ1:4
-
ይላል።
ታዲያ እነዚህ የእግዚአብሔር ምርጦች #በክርስቶስ ናቸው።
#በክርስቶስ #ኢየሱስ ላሉት ደግሞ #ኩነኔ የለባቸዎም << #በክርስቶስ #ኢየሱስ #ላሉት አሁን #ኩነኔ የለባቸውም >>ሮሜ8:1
#በክርስቶስ #ኢየሱስ የሆኑት እነዚህ የእግዚአብሔር ምርጦች አሁን #ኩነኔ #የለባቸውም#ኩነኔ #የሌለባቸውን እነዚህን ምርጦች ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም
#ሊኮንናቸው አይችልም።
ለምን? ምክንያቱም ለእነርሱ ሲል #የሞተ አለ ፣ለእነርሱ
ሲል #ከሞት የተነሳ አለ ፣ለእነርሱ ሲል #በእግዚአብሔር ቀኝ #የተቀመጠ አለ
፣ ለእነርሱ ሲል #የሚማልድ #ሊቀ #ካህናት አለ እርሱም #ክርስቶስ #ኢየሱስ ነው።
የእግዚአብሔር ምርጦች #ከኩነኔ #ነጻ የመሆናቸው #ማረጋገጫ በክርስቶስ ሞት
#ትንሣኤ#እርገት እና #ምልጃ ነው ።
#እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም #አይኮንናቸውም
ምክንያቱም ለእነርሱ ሲል #የሞተ አለ እርሱም #ክርስቶስ ነው።
#ክርስቶስ #ለምርጦቹ ሲል በደላቸውን ተሸክሞ በእንጨት ላይ #ሞቷል#በበደላቸው
የሚመጣባቸው #ፍርድ እሱ #ተሸክሟል #ፍርዱም #በሞቱ ተፈጽሟል ፣ታዲያ
#ክርስቶስ #ኢየሱስ የሞተላቸውን እነዚህን ምርጦች ማነው #የሚኮንን?
ከእግዚአብሔር ጋር በክርስቶስ #ሞት #ታርቀዋል /ሮሜ5:8/
ታዲያ ማነው #የሚኮንናቸው? ስለእነርሱ #መሞት ብቻ አይደለም ይልቁንም ስለ እነርሱ #ከሞት #ተነሥቷል ፣ለምን #ከሞት ተነሣ? ።
< #እኛን #ስለማጽደቅ #ከሙታን #ተነሣ> /ሮሜ4:24/
ተብሏል።
#ከሞቱ በበለጠ #ትንሣኤው #ከኩነኔ #ለመዳናቸው ትልቅ ዋስትናቸው ነው። እነርሱን #ለማጽደቅ ከሞት #ተነስቷል #በትንሣኤውም #ጸድቀዋል ፣በክርስቶስ
#ትንሣኤ #የጸደቁትን እነዚህን የእግዚአብሔር ምርጦች #ማን #ይኮንናቸዋል?
እነዚህ ምርጦች #ከእግዚአብሔር ጋር #በልጁ #በክርስቶስ #ሞት #ታርቀዋል
ይልቁንም #ከሞት #ተነስቶ ሕያው ሆኖ በመኖሩ በህይወቱ ደግሞ ይድናሉ ፦
< #ከእግዚአብሔር ጋር #በልጁ ሞት #ከታረቅን #ይልቁንም ከታረቅን በኋላ #በሕይወቱ #እንድናለን> /ሮሜ5:11/
#ክርስቶስ ባይነሳ ኖሮ #ጽድቃቸው አይረጋገጥም
ነበረ ኃጢአተኛ ሆነው ይቀሩ ነበር << #ክርስቶስ #ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት
እስከ አሁን ድረሰ #በኃጢአታችሁ #አላችሁ>> /1ኛቆሮ15:17/ #በክርስቶስ ትንሣኤ
ዘለለማዊ #ጽድቅ አግኝተዋል።
#እግዚአብሔር #በልጁ #ትንሣኤ #ያጸደቃቸውን
ምርጦቹን ማን #ይኮንናቸዋል? ማንም። ስለዚህ #የክርስቶስ #ትንሣኤ #ከኩነኔ #የሚድኑበት ማረጋገጫቸው ሆኗልና የእግዚአብሔርን ምርጦች ማንም
#አይኮንናቸውም
#ይህም ብቻ አይደለም #ክርስቶስ ወደ #ሰማይ አርጎ
#በእግዚአብሔር ቀኝ መቀመጡም ታላቅ የደኅንነት #ማረጋገጫቸው ነው።
#ክርስቶስ ወደ ሰማይ የወጣው #የሰዎችን ሥጋ #እንደያዘ ነው።
<< #ወደላይ
#በወጣህ ጊዜ ምርኮን ማረክህ>> /ኤፌ4:7/ እንደተባለ ክርስቶስ #በኃጢአት #በሕግ
#በሞት #በሰይጣን እንዲሁም ከማንኛውም ጠላት ሥር የነበረውን #የሰውን ሥጋ
ከጠላት ማርኮ በድል አድራጊነት ይዞት #በሰማያዊ ሥፍራ #በቀኙ ሥጋችንን #ሲያስቀምጠው በእርሱ #በኩል ከሞት በላይ መሆናችን ማንም ዝቅ ሊያደርገው
#በማይችል ከፍታ ላይ #መሆናችን ሲታወቅ በእርግጥም በእንዲህ አይነት ከፍታ
#ከፍ ያደረጋቸውን የእግዚአብሔር ምርጦች ማንም #ሊኮንናቸው አይችልም።
<< #ከክርስቶስ ጋር አስነሳን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ #ስፍራ ከእርሱ ጋር
#አስቀመጠን >> /ኤፌ2:7/ለው
ያለውም ይህን ነው ።
#ስለ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት #ይታይላቸው ዘንድ
ወደ ሰማይ #ገብቷልና #ማንም #ይኮንናቸው ዘንድ አይችልም
/ዕብ9:24/

እግዚአብሔር መርጦ #ያጸደቀንን ማን #ይከሰናል? #ክርስቶስ #ለኃጢአታችን
#የሞተልንን ማን #ይኮንነናል? #ክርስቶስ እኛን #ለማጽደቅ ከሞት ተነስቷል ታዲያ
ማን #ይኮንነናል? ስለ እኛ በእግዚአብሔር ፊት #ይታይ ዘንድ ወደ ሰማይ
ገብቷልና ማን #ይኮንነናል? ክርስቶስ #ስለ እኛ #ይማልዳልና ማን ይኮንነናል?

አሜን ሃሌ ሉያ። ማንም

የክፍሉ ዓብይ ሀሳብ ይህ ነው። ይህንን ከተረዳን። ነገ ደግሞ ስለዚህ ጥቅስ የተነሱትንና የተባሉትን የተለያዩ ኑፋቄዎች እንመለከታለን።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ዕብራውያን 5፤ 7-10 << እርሱም #በስጋው #ወራት #ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ #ጩኸትና #ከእንባ ጋር ጸሎትንና #ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፤ ምንም ልጅ ቢሆን፥ ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤ ከተፈጸመም በኋላ በእግዚአብሔር እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ ስለ ተጠራ፥ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት ሆነላቸው።>> አንዳንዶች…


ዕብራውያን 7፤ 20-28

<< እነርሱም ያለ #መሐላ #ካህናት ሆነዋልና፤ #እርሱ ግን። ጌታ። አንተ #እንደ #መልከ ጼዴቅ ሹመት #ለዘላለም #ካህን ነህ ብሎ #ማለ #አይጸጸትም ብሎ በተናገረለት #ከመሐላ ጋር #ካህን ሆኖአልና ያለ #መሐላ #ካህን እንዳልሆነ መጠን፥ እንዲሁ #ኢየሱስ #ለሚሻል #ኪዳን #ዋስ ሆኖአል። #እነርሱም እንዳይኖሩ #ሞት ስለ ከለከላቸው #ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤ #እርሱ ግን #ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ #የማይለወጥ #ክህነት አለው፤ #ስለ እነርሱም #ሊያማልድ #ዘወትር #በሕይወት #ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ #በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ #ሊያድናቸው ይችላል። #ቅዱስና ያለ #ተንኮል ነውርም #የሌለበት ከኃጢአተኞችም የተለየ #ከሰማያትም ከፍ ከፍ ያለ፥ እንደዚህ ያለ #ሊቀ #ካህናት ይገባልና፤ #እርሱም እንደነዚያ #ሊቃነ ካህናት አስቀድሞ ስለ ራሱ #ኃጢአት በኋላም ስለ ሕዝቡ #ኃጢአት #ዕለት #ዕለት #መሥዋዕትን ሊያቀርብ #አያስፈልገውም፤ ራሱን #ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ #ፈጽሞ #አድርጎአልና። ሕጉ ድካም ያላቸውን ሰዎች #ሊቀ #ካህናት #አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣ #የመሐላው #ቃል ግን ለዘላለም #ፍጹም የሆነውን ልጅ ይሾማል።>>


<<ለሚሻል ኪዳን ዋስ>> የሆነው #ክርስቶስ እስከሚመጣ ድረስ #ሞት #በአገልግሎታቸው እንዳይቀጥሉ #የከለከላቸው 83 #ሊቃነ #ካህናት ተሹመው ነበር። በቀደመው ኪዳን ውስጥ የነበሩ #ሰዎች አገልግሎት ፈልገው <<አንድ ሰው ተቸግሮ #ካህን ፍለጋ ምናልባት ይሄዳል። ሲድርስ ግን < #ኸረ ሞቶአል! እሌላ ዘንድ መሀድ ያስፈልግሀል> ይባልና ሰውዬው #ዐዝኖ ይሄዳል። #በኢየሱስ ግን እንደዚ የለም፤ #በፈለግህበት ጊዜ ፣ #ባለህበት ቦታ #እርሱ በዚያ አለ>>።
📖/፤ ዳ.እ፣ የሐዋርያው የጳውሎስ መልእክት ወደ እብራውያን ትርጓሜ (ጎንደር፣ 1995 - 5ተኛ እትም) ገጽ 53።
📖/፤ GBV፣ የዕብራውያን መልእክት አንድምታ (ትርጓሜው ከነንባቡ)፣ (1998) ገጽ 61።

#በእግዚአብሄርና #በሰው መካከል እንዲሆኑ #ተስፋ የምናደርጋቸው (የካህኑን ሥራ እንዲሠሩ የምንጠብቀቸው) በሙሉ #በምድር በነበሩ ጊዜ (ከሥጋ ሞታቸው በፊት) በነበረው #አገልግሎታቸው እርሱን ሲያከብሩና #በእርሱ #የክህነት #አገልግሎት ሲጠቀሙ የነበሩ ናቸው። ምናልባት እነዚህ #ሰዎች #በአገልግሎት #ዘመናቸው #ካህናት የነበሩ ቢሆኑም እንኳ አሁን ግን #ሞት ከዚህ አገልግሎታቸው #ሽሯቸዋልና #ከእንግዲህ በዚህ በኩል #ሊያገለግሉ አይችሉም። ስለዚህ #ሞት ወደማይያዘው፣ #ክህነቱም #ዘለዓለማዊ ወደ ሆነው #ጌታ መጠጋት የተሻለ #ውሳኔ ነው።
#መድኃናችን @ክርስቶስ <<አስቀድሞ ስለራሱ ኃጢአት>> ያቀረበው #መስዋእት የለም። ምክንያቱም እርሱ #ቅዱስ#ንጹሕ#ነቀፋ የሌለበት፣ #ጻድቅ ነውና #ክህነቱም ነቀፋ የለበትም። እንዲህ ያለው #ቅዱስ ስለእኛ #በደል ራሱን #መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ <<ምንኛ #የከበረ #መሥዋዕት ነው፤ ለሰዎች ሁሉ #ደኅነንትን ለመስጠት #ኢየሱስ #ሕይወቱን #መሥዋዕት አደረገ። ኢየሱስ ወደዚህ #ዓለም የመጣው #ሕይወቱን ለብዙዎች #ቤዛ አድርጎ #ለመስጠት ነው (ማርቆስ 10፥45)። በመጨረሻም ከመሞቱ በፊት በነበረው ምሽት <<ይህ ስለ ብዙዎች የሚፈስ #የዐዲስ ኪዳን #ደሜ ነው> አለ (ማርቆስ 14፥24)። ለዚህ ነው #በኢየሱስ #ሞት፥ ባፈሰሰው #ክቡር #ደም ድነናል ብለን የምንመሰክረው>>።

በቀደመው ኪዳን አንዱ #ካህን #ሞቶ ሌላው #እስከሚሾም ድረስ #ካህን የማይኖርበት ጊዜ መፈጠሩ እርግጥ ነው። ይህ ደግሞ #በካህኑ አማካይነት ይደረግ የነበረው #የዕርቅ #ሥርዐት ምን ያህል #ችግር ያለበት እንደ ሆነ አመላካች ነው። የእኛ #ሊቀ ካህናት #ኢየሱስ ግን #ዘላለም #በቦታው ስላለ በእርሱ የሚያምኑት #ካህን የሚያጡበት ምንም #ምክንያት የለም። እኛስ ከዚህ #ታላቅ #ሊቀ ካህን ወደ የት እንሄዳለን? መጽሀፉም << #ቅዱስና ያለ #ተንኮል #ነውርም የሌለበት #ከኃጢአተኞችም የተለየ #ከሰማያትም #ከፍ #ከፍ ያለ፥ እንደዚህ ያለ #ሊቀ #ካህናት ይገባልና፤>> የሚለው ለዚሁ ነው(ቁ.26)።

ምንባቡ <ፍጹም ሰው> ስለሆነው ስለ #ኢየሱስ እየተናገረ፤ ለዚህም ደግሞ በቀደመው ኪዳን እና #በእርሱ #ክህነት መካከል ያለውን #ልዩነት እያቀረበ <<ጌታችን ከይሁዳ ነገድ እንደ ወጣ የተገለጠ ነው>> እያለ (ቁ.14) << #በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ #ሊያድናቸው ይችላል>> ብሎ እያስተማረ (ቁ.25) መሆኑን እየተመለከቱ፤ <<በመቀጠል "ውውእቱስ ይነብር ለዓለም እስመ ኢይሠዐር ክህነቱ" (እርሱ ግን #ለዘላለም ይኖራል፤ ክህነቱ አይሻርምና) በማለት የካህናተ ሓዲስ አለቃ #ኢየሱስ #ክርስቶስ ግን <ዘለዓለማዊ አምላክ> ነውና መሻር መለወጥ የሌለበት ክህነቱም የማይለወጥ እንደሆነ ጻፈልን>> የሚሉ ሰዎች ክፍሉ ስለ #ክርስቶስ #አምላክነት እንደማይናገር ሳይገባቸው ቀርቶ ሳይሆን #ነገረ #ምልጃውን #ለመሸፈን መሆኑ ግልጽ ነው።
📖/፤ ሮዳስ ታደሰ (መጋቤ ዐዲስ)፣ ነገረ ክርስቶስ ክፍል 1 (የካቲት 2008) ገጽ 491።

ሐዋርያው አይሻርም ያለው #ክህነቱን እንጂ #መንግስቱን እንዳልሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል። ደግሞስ በራሳቸውም ሆነ በ2000 በታተመው 80 አሀዱ <<ለዘላለም ሕያው ነውና ያስታርቃቸዋል>> የሚል መስፈሩን እንዴት አላዩት ይሆን? በአንድምታውስ <<በእሱ አስታራቂነት ወደ እግዚአብሔር። የቀረቡትን ማዳን ይቻለዋል። ፈጽሞ ሕያው ነውና። ተንበለ ሲል፤ አንድም በቁሙ በዕለተ ዐርብ ባደረገው ተልእኮ እስከ ምጽአት ድረስ ሲያድንበት የሚኖር ስለ ሆነ>> መሆኑን መስፈሩን ምነው ሳያነቡት ቀሩ?
📖/፤ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሐፍ ንባቡና ትርጓሜው (አ.አ፣ ግንቦት 1988) ገጽ 434
📖/፤ መሐሪ ትርፌ (ሊቀ ሊቃውንት)፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሐፍ ንባቡ ከነትርጓሜው (አ.አ፣ ጥቅምት 23 1948) ገጽ 647።
(⁉️ ተንበለ ፦ <<መለመን፣ መጸለይ፣ መማለድ፣ ማማለድ፣ ማላጅ፣ አማላጅ መሆን፣ ዕርቅ ፍቅር ይቅርታ መፈለግ፣ ማረኝ ማርልኝ ማለት>>
📖/፤ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ (አለቃ) መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ዐዲስ(1948) ገጽ 900)።
ታድያ #በ80 አሀዱም ሆነ #በአንድምታው ላይ #አስታራቂ መሆኑ የሰፈረው እርሱ ራሱ #አምላክ አይደል እንዴ? ከማን ጋር ነው #የሚያስታርቀው? (ይታረቃቸዋል ሳይሆን ያስታርቃቸዋል የሚለው አገላለጽ ዕርቁ የሚከናወነው ከሌላ አካል ጋር እንደ ሆነ ነው የሚያስረዳው)

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ለ"ማርያም" ለሚለው ስም የተሰጡ #ትርጉሞች #የቤተስክርስቲያን #አባቶችም ሆኑ #ወጣት #ሰባኪያንና #ህዝቡም በብዛት የሚያውቁት #የተለመደ #ትርጉም ነው። የሚገርመው ደሞ #የስሙ #ትርጉሞች ብዙ #ማርያም የተባሉ #ሴቶች እያሉ ማእከል ያደረገው ግን #የጌታችን #እናት #ድንግል #ማርያምን ብቻ ይመስላል። እነዚን #ትርጉሞች ይዘን ለሌሎች < #ማርያም> ለተባሉ #ሴቶች ትርጉሙን…
▶️ ከላይ እንዳየነው አንዳንዶች #የስሙን ሙሉ #ሐረግ ተከትለው ሌሎች ለሁለት ከፍለው #ለመተርጎም ከሞከሩት #ውጪ ሌሎች ደግሞ ከዚህ በተለየ መንገድ #ማርያም የሚለውን ስም #ለማብለጥ ወይም #ከፍ #ለማረግ ሲሉ #ማርያም ስለሚለው #ስም #ትርጉም #የአማርኛውን ወይም #የግእዙን ሆህያት ብቻ ተከትለው #ፊደል #በፊደል እየከፋፈሉ #በግእዝ ቋንቋ #በግጥም መልክ ይተረጉማሉ።👇👇

✳️👉 ማኅደረ መለኮት [የመለኮት ማደሪያ]።
✳️👉 ርግብየ ይቤላ [ንጉስ ሰለሞን ርግቤ ያላት፥ መኃ 6፥9]።
✳️👉 ያንቀዓዱ ኅቤኪ ኩሉ ፍጥረት [ሁሉም ፍጥረት ወደ አንቺ ያንጋጥጣል(ያቀናል)]።
✳️👉 ምስአል ወምስጋድ [ወምስትሥራየ ኃጢአት፣ የምንለምናት፣ የምንሰግድላት[4]]።

️ይህም #ትርጉም ከላይ እንዳልነው #የአማርኛ #ፊደላትን #በግዕዝና #በግጥም #የመተርጎም ሙከራ ሲሆን ይህም እንደሌሎቹ #ትርጎሞች ለሌሎች " #ማርያም" የሚለው #ስም ላላቸው የሚያገለግል አይመስልም። እንዲህ አይነቱ #ትርጉም የመስጠት አካሄድ ደግሞ #ከዓውደ #መሠረቱ ያስወጣል።

️በዚህ #ትርጉም መሠረት " #ማርያም ማለት #የመለኮት #ማደሪያ የሆነች፤ ንጉስ ሠሎሞን #በመኃልይ #መኃልይ መጽሐፉ #ርግቤ ያላት፤ ፍጥረት ሁሉ ወደ እርሷ #የሚያቀኑ#የሚሰግዱ#የሚለምኑ እና እርሷም #ለምላሹ #ኃጢአትን #የምታስተሰርይ ናት" ማለት በግልጽ #ማርያምን #ማምለክ ማለት ነው። #አምልኮ ከዚህ ውጪ #ካለ ንገሩን!!

▶️ መቼም #ሰይጣን በተለይም #በኢትዮጵያ #በ15ኛው ክፍለ ዘመን ጊዜና ባለስልጣናት ገጥሞት በብዙ #ሠይፍ < #የማርያምን #ምልጃ> ትምህርት ወደ #ቤተክርስቲያን አስገብቶ #ማርያም ባትሰማቸውም ወደ እርሷ #የሚያንጋጥጡ#የሚሰግዱ#የሚለምኑ#ኃጢአታቸውን #የሚናዘዙ ይብዙ እንጅ #በመጽሀፍቅዱስ ታሪክ እንኳን #ወደእሷ ወደየትኛውም #ፍጡር #የጸለየ አናገኝም።

▶️ ደግሞ #ሰሎሞን #በመኃልየ #መኃልይ መጽሐፉ ሱናማይት{ሱናማጢሳዊት} የሆነችውን አንዲት ልጃገረድ #ውዴ#ርግቤ#መደምደሚያየ እያለ በፍቅር እንዴት #አሸንፎ ወደ ቤቱ እንዳመጣትና #ባሸበረቀ አልጋው ላይ አጋድሞ #ጡቶቿ እንዴት እንዳረኩት እርሷም በእርሱ እንዴት #እንደረካች የሚናገረውን #የፍቅር #ኃይልና ግለት #የተንጸባረቀበትን መጽሐፍ ወስዶና #በጥሶ <ሰሎሞን #ርግቤ #መደምደሚያዬ ያላት #ማርያምን ነው> ማለት ምናልባት መጽሐፉንና #ዓላማውን #ካለማንበብና #ካለማወቅ የመነጨ፣ አሳፋሪም ጭምር መሆኑን #የሱናማይቷ ሴት #ለፍቅር ስሜት የመጦዝ ባህሪ ታላቅ አድርገው ለሚገምቷት "ለቅድስት ድንግል ማርያም" ባልተስማማ ነበር።

▶️ መኃልየ #መኃልየ መጽሀፍም #የብሉይኪዳን ክፍል እንደመሆኑ #በሰለሞንና #በማርያም መካከል ያለውን "የዘመን ልዩነት" መገመት ራሱ አይከብድም። #ማርያም #በሰለሞን ዘመን ፈጽማ ያልነበረችውን፤ #ሰለሞን እንዴት በወቅቱ ከነበሩት < #ስልሳ ንግሥታት #ሰማኒያም ቁባቶች(ውሹሞች) #ቁጥር የሌላቸው ቆነጃጅቶች> ጋር #በውሽምነት መልኩ ሊቆጥራት ይችላል? {መኅልየ 6፥8}

▶️ ደግሞ < #የዓለምን #ኃጢአት ሊያስወግድ የተገለጠ #የእግዚአብሄር #በግ> {ዩሐ 1፥29 , ራዕ 5፤5-10} #ኃጢአትን #የማስተሰረይ ስልጣንም #የኢየሱስ #ክርስቶስ ብቻ እንደሆነ እያወቅን {ማር 2፤10} ማርያምን "ወምስትሥራየ ኃጢአት" {ኃጢአትን የምታስተሰርይ} እንዴት ልንል እንችላለን?? #በኃጢአት ላይ የወጣውን #የእግዚአብሄርን #ቁጣ #ፍርዱን #ሊያቃልለው ወይም #ሊያስተወው የሚችልስ ጉልበተኛ ማነው? #ሙሴ እንኳ በምድር ህይወቱ #የእስራኤልን #ኃጢአት ተከራክሮ #ለማስቀረት ቢሞክርም #እግዚአብሔር #ፍርዱን መለወጥ ባለመቻሉ በርካቶች #ሞተዋል። {ዘዳ 32፤30-35}። #ኃጢአተኛው እራሱ #ካልተመለሰና #ንስሐ ካልገባ በቀር #እግዚአብሔር ኃጢአትን ይጠላል #ይቀጣልምም {ዩሐ 8-24}።