ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ መጽሀፍ ቅዱስ #የእስራኤል #ዜግነት ያላት #እስራኤላዊት#በገሊላ ናዝሬት ከተማ ትኖር የነበረች #አይሁዳዊት ወጣት ሴት እንደነበረች ይናገራል [ሉቃ 1፥26] እንዲሁም #ከዳዊት #የዘር #ግንድ የተገኘች መሆኗንም ይናገራል [ማቴ 1፥17 ፣ ኢሳ 11፥1 ፣ ሐዋ 13፥22]።

▶️ ዘመዷ #ኤልሳቤጥ ስትሆን ምን አይነት #ዝምድና እንደነበራቸው ግን በግልጽ የተቀመጠ ነገር የለም [ሉቃ 1-36]። ስለማርያም #ቤተሰቦች #የእነማ ልጅ እንደሆነች፣ የትና መቼ #እንደተወለደች፣ የት #እንዳደገች #መጽሀፍ ቅዱስ አላማው ስላልሆነ የተወሰነ #ፍንጭ ከመስጠት በስተቀር ምንም #አይናገርም
#መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤልም #ኢየሱስ ክርስቶስን እንደምትወልድ #ካበሰራት ቡሀላ እንኳ " #ከመውለዷ ጋር በተያያዘ ካልሆነ በቀር #ሰፋ ያለ መረጃ የለም።

▶️ እንደዛ ሆኖ ሳለ #መጽሀፍቅዱስ #ዝም ያለበትን ነገር #ዝም ማለት ሲገባቸው #የመጽሀፍቅዱስን አላማ ሳይገነዘቡ #ግምታዊ #ሃሳቦችን በመስጠት #የተጻፉና #በየአደባባዩ የሚሰበኩ መጽሀፍት #ጥቂቶች አይደሉም።
<< ድንግል ማርያም #ኢትዮጽያዊት ነች>> ብለው በድፍረት የጻፉም እንዳሉ ይታወቃል።
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
📖፤ / ሱረቱ መርየም 19፤ 27-28 (2ተኛ እትም 1998 ዓ.ም) *ሱራህ 19, አያህ 27* فَأَتَتْ بِهِۦ قَوْمَهَا تَحْمِلُهُۥ ۖ قَالُوا۟ يَٰمَرْيَمُ لَقَدْ جِئْتِ شَيْـًۭٔا فَرِيًّۭا በእርሱም የተሸከመቺው ሆና ወደ ዘመዶቿ መጣች፡፡ «መርየም ሆይ! ከባድን ነገር በእርግጥ ሠራሽ» አሏት፡፡ *ሱራህ 19, አያህ 28* يَٰٓأُخْتَ هَٰرُونَ…
▶️ ሌሎች #በኦርቶዶክስ ያሉ #መጽሀፍቶች ደግሞ የተለያዩ #የዘር ግንድ ቆጠራዎችን ይጠቅሳሉ።
" #ድርሳነ #ጽዮን" የተባለው መጽሀፍ #የማርያም የዘር ሃረግን ሲገልጽ👇
ሜሊኪ። "የሐና(የእናቷ)
/ \ |
ሴም ሌዊ። ኤሊ
| |
ሆናሲን። ሜሊኪን
| |
ቀለምዮስን። ማቴን
| |
ኢያቄምን። ሐና
\ /
ማ ር ያ ም ን
ወለዱ ይላል[7]።

▶️ የማቲዎስ ወንጌል እንድምታ ደግሞ ከዚህ የተለየ ይገልጻል።
አኪም
|
ኤልዩድ
|
አልዓዛር
|
ቅዕራ
|
ኢያቄም ይላል[8]።

እንግዲህ እነዚህ #መጽሀፍት ደግሞ #በማርያም #አባት ቢስማሙም #በአያቶቻቸው ግን ፈጽሞ #አይስማሙም

▶️ የአንዳንድ ካቶሊካውያን አመለካከትም። << #ማርያም #ሰማያዊ #ፍጡር>> እንደሆነች ሲገልጹ ይህንንም ሀሳብ #የሰዓታት ጸሐፊና #የተአምረ #ማርያም ጸሐፊም በከፊል የሚቀበሉት ቢሆንም #ሃይማኖተ #አበው ግን በግልጽ ይህን ሃሳብ ያወግዘዋል። << እመቤታችን ከሰው የተለየች #ፍጥረት #ምድራዊት ያልሆነች ቀድሞ #በሰማይ #የነበረች #ሃይል(ፍጡር) ናት የሚል ቢኖር #ውግዝ ይሁን። በቅድስት መጽሀፍት እንደተጻፈው #ቅድስት ድንግል ማርያም #ከዳዊት#ከይሁዳ #ከአብርሃም ዘር እንደሆነች #በእውነት የሚያምን ግን #ከግዝት የተፈታ ይሁን>> ይላል[9]።

▶️ ማርያም ዘመዷ #ኤልሳቤጥ፣ እጮኛዋም #ዮሴፍ የነበረ ሴት እንደሆነች ሃገሯም #ናዝሬት #ገሊላ ሆኖ #ከዳዊት #ዘር እንደነበረች #መጽሀፍቅዱስ እየተናገረ #ሰማያዊ #ፍጡር #ናት ማለት " ህዝቤ #እውቀት #ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል/ሆሴ 4-6/። እንደሚለው #የእውቀት #ማጣት ይመስላል።
መጽሀፍቅዱስ የማርያም #አባት #ኢያቄም ሳይሆን < #ኤሊ> የተባለ #ሰው እንደነበር የሚገልጸው ፍንጭ አለ።
(በሉቃስ 3፥23)
ደግሞ #የማርያም #ገድሎች እንደሚሉት #ለእናት #ለአባቷ #አንዲት #ልጅ ሳትሆን #እህትም እንዳላት #መጽሀፍቅዱስ ይናገራል። 👇

<< ጭፍሮችም እንዲህ አደረጉ ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ #የእናቱም #እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።>> {ዮሐ19፥25}።

<<ለዮሴፍ አባቱም #የማታን ልጅ #የያዕቆብ ልጅ (የማታን የልጅ ልጅ) ነው ብሎ #ማቲዎስ (በማቲ 1-16) #የዘር #ሐረጉን ሲቆጥር ወንጌላዊው #ሉቃስ ደግሞ #የማርያምን #የዘር ሃረግ ተከትሎ #በመቁጠር #የማርያም #አባቷ < #ኤሊ> እንደሆነ አስቀምጧል {ሉቃ 3-23}።

🔆 የዮሴፍ የዘር ሀረግ 🔆

(የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 1)
----------
1፤ የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።

2፤ አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ........
............................................

6፤ " እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።"...............................
............................................

15፤ ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ፤ አልዓዛርም #ማታንን ወለደ፤ ማታንም #ያዕቆብን ወለደ፤

16፤ ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ #ዮሴፍን ወለደ።
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ነብያት#ካህናት#ሐዋሪያት #ሁሉም ማለት ይቻላል ጸልየዋል። #ጸሎታቸውም በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር እንጂ እንኳን ወደ #ፍጡራን፣ ወደ #መላእክት የጸለየ አንድም #ሰው አናገኘም። #ድንግል #ማርያም እንኳን #በሉቃስ 1፤46-55 እንደተገለጸው <<ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፤ መንፈሴም በአምላኬ በመድሃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች.....>> በማለት እንዲሁም #በሐዋ 1፥25 #ከ120 #ሰዎች ጋር አብራ <<የሁሉንም ልብ የምታውቅ ጌታ ሆይ>> እያለች በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ነው የጸለየችው። #ኢየሱስ ክርስቶስም #በሥጋው ወራት #በርካታ ጊዜ ያለማቋረጥ ወደ #አባቱ <<አባት ሆይ...>> በማለት #ጸሎት አድርጓል [ዩሀ 17፥1]። #ክርስቶስ አገልግሎቱን #በጸሎት ጀምሮ [ማቴ 4፥1] በመስቀል ላይ #ነፍሱን ሲሰጥና #አገልግሎቱን ሲደመድም #በጸሎት ውስጥ ነበር። እርሱ እንዳደረገውም #እንዳስተማረን <<አባታችን ሆይ>> ብለን እንድንጸልይ እንጂ <<እመቤታችን ሆይ>> ብለንም ሆነ #ወደሌላ #እንድንጸልይ አላስተማረንም።

▶️ ክርስቶስ ስለ #ጸሎት ሁኔታ ከሰጠን #መመሪያዎች ውስጥ <<አንተ ግን ስትጸልይ ወደ እልፍኝ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሀል>> [ማቴ 6፥6] ብሎ ነው ያዘዘን። #ሐዋሪያትም ቢሆኑ #ከክርስቶስ የተማሩትን #ትምህርት #አብነት (ምሳሌ) አድርገው <<የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ...">> [ #ሐዋ 1፥25]፣ <<ጌታ ሆይ አንተ ሰማዩንና ምድሩን ባሕሩንም በእርሱም የሚኖረውን ሁሉ የፈጠረህ...>> [ #ሐዋ 4፥24] ፣<<ጌታ ኢየሱስ ሆይ...>> [ #ሐዋ 7፥59]..ወ.ዘ.ተ በማለት #ቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ብቻ ነው የጸለዩት። ስለሆነም እንደ እነርሱ #መጽሀፍቅዱስ <<በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ>> በሚለው መመሪያ መሰረት [ #ፊል 4፥6] ወደ #እግዚአብሔር #ቀጥታ እንድንጸልይ ያሳስበናል።

▶️ ጸሎት በራሱ #የቃሉ #ትርጉም #ከእግዚአብሄር ጋር #መነጋገር ማለት እግዚአብሔርን #ማክበር [ራዕ 4፤ 10-11] እግዚአብሔርን #ማመስገን [መዝ 106(107) ፤1-2] እግዚአብሔርን #መለመን [ያዕ 1፤5] እግዚአብሔር የሚናገረውን #ማዳመጥ [መዝ 84(85) ፤8] ማለት ነው። ለዛም ነው ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ ያለው <<ሥጋ ለባሽ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል።>> ያለው [ #መዝ 65፥2]። በዚህም መሰረት በብሉይ ኪዳን #አዳም#ኖህ#አብርሃም#ይስሐቅ#ያዕቆብ#ዮሴፍ#ሙሴ#ኢያሱ#የሳሙኤል እናት #ሐና#ሳሙኤል#ጌድዮን#ባርቅ#ሳምሶን#ዮፍታሔ#ዳዊት#ሰለሞን#ኤልያስ#ኤልሳዕ#ኢዮስያስ#ሕዝቅያስ#ኢሳይያስ#ኤርምያስ#ኢዮብ#ዕዝራ#ነህምያ#አስቴር#ዳንኤል#ሕዝቅኤል#ዮናስ . . .ወዘተ በሐዲስ ኪዳንም 12ቱ #ደቀመዛሙርት#ድንግል ማርያም፣ #ዘካርያስ#ስምዖን#ጳውሎስ#ጴጥሮስ፣ በህብረት ደግሞ #ጳውሎስና #ሲላስ#ሐዋርያት #በአንድነት፣ ራሱም #ኢየሱስ ክርስቶስ #በሥጋዌ ማንነቱ፣ እጅግ #ኃጢአተኞች ተብለው የሚቆጠሩት #በክርስቶስ ቀኝ የተሰቀለው #ወንበዴና ከሰፈር ውጭ ተጥለው የነበሩት #ለምጻሞች ሁሉ #ጸልየዋል። የጸለዩትም #ጸሎት #በቀጥታ ወደ #እግዚአብሔር ሆኖ የከበረ #መልስ ማግኘታቸውም ሁሉ ለትምህርታችን #ተጽፏል። ስለዚህ ወደ #ማርያምም ሆነ ወደ ማንኛውም #ፍጡር መጸለይ #ኢ #መጽሀፍ ቅዱሳዊ ዘመን አመጣሽ #ተግባር ነው። ደግሞም ዛሬ በአንዳንድ #ምእመናን እንደሚታየው ከላይ የጠቀስናቸው ሁሉ #ለመጸለይ #የልባቸውን #ጩኸት አቀረቡ እንጂ #ለጸሎት ብለው የተጠቀሙበት #የጸሎት #መጽሐፍ <<የሰኞ የማክሰኞ>> ወ.ዘ.ተ እያሉ የሚደግሙት #መጽሐፍ አልነበራቸውም። #በብሉይ ኪዳን ተጽፎ የነበረው #የመዝሙረ ዳዊት #መጽሐፍ #ኢየሱስ ክርስቶስና #ሐዋርያት ለትምህርቶቻቸው ይጠቅሱት ነበር እንጂ #ለጸሎቶቻቸው #ድጋፍ አድርገው አልተጠቀሙበትም። ስለዚህ #ጸሎት #ከልብ የሚመነጭ ስለሆነ በየቀኑ በብዙ #ገጾች የሚቆጠሩ የተለያዩ #ርዝመት ያላቸውን የተጻፉ #መጽሀፍትን #ማዘጋጀትና#መደጋገም እንዲሁም #ህመም ሲሰማቸው #መጽሀፍቶቹን #መተሻሽት#በራስጌ ላይ #ማንጠልጠል#በአንገት ላይ #ማነገት አይደለም።

▶️ ጌታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን #የፈሪሳውያን (የአህዛብ) #ጸሎት #ስነ - ሥርዓት <<አህዛብም በመናገራቸው #ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና #ስትጸልዩ እንደ እነርሱ #በከንቱ አትድገሙ ስለዚህ አትምሰሏቸው>> በማለት ተቃውሟል [ማቴ 6፤ 7-8]። ስለዚህ #ጸሎት ሰዎች በደረሱልን የ"ጸሎት" #ድርሰት #መጽሀፍ ወይም የሌሎችን #ጸሎት በመድገም #መጸለይ ሳይሆን እንደ ጌታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ #እግዚአብሔር በመቅረብ የልባችንን #ጸሎት #በእውነትና #በመንፈስ #ከአክብሮት ጋር በማቅረብ ነው [ማቴ 26፤ 39-44 ፣ ዩሀ 17፤ 1-26]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆
▶️ እንግዲህ ከላይ እንዳየነው #በጥንት #ስነ ፅሁፎች ውስጥ #ሥዕሎች ወይም #ሃውልቶች #ይናገራሉ ብሎ መቁጠር ወይም #እንደተናገሩ አድርጎ መናገርና ሌሎች #ምትሃታዊ ነገሮችንም ያደረጋሉ በሚል ሰፊ #እምነትና #ማስፈራራት ነበር። #መጽሀፍቅዱስ ግን ይህን #ሁኔታ በማያሻማ መልኩ #የአውሬው {የዳቢሎስ} #ተግባር እንደሆነ ይገልጻል {ራዕ 13፥15}።

▶️ ከላይ #ከተጠቀሱት ጥቂት #ማስፈራሪያዎች ሌላ #ስዕሎች ተቀባይነት እንዲኖራቸው #ስዕሎቹ ፊት #መጸለይና #መስገድ የተለየ #በረከት ያስገኛል ብሎ #በማጓጓትና #ለአማናዊቷ #ማርያም #የመስገድ ያክል ይቆጠራል የሚል #አብይ #ምክንያትም አለ።