ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram


ሮሜ 8÷34

" #የሞተው÷ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው÷ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው÷ ደግሞ ስለ እኛ #የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡"

#ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ መልእክቱ ማስተላልፍ የፈለገው ‹‹ #እንግዲህ #በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን #ኵነኔ የለባቸውም›› የሚለውን ነው (ቊጥር 1)፡፡ ሐዋርያው በመቀጠል ‹‹ #በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው #የሕይወት መንፈስ ሕግ #ከኀጢአትና #ከሞት ሕግ ዐርነት›› ያወጣን መሆኑን ያበሥርና (ቊጥር 2) እንደ #ሥጋ ፈቃድ ሳይሆን እንደ #መንፈስ ፈቃድ መመላለስ እንደሚገባን ይመክራል፡፡ ምክንያቱንም ደግሞ ‹‹ስለ #ሥጋ ማሰብ #ሞት ነውና÷ ስለ #መንፈስ ማሰብ ግን #ሕይወትና #ሰላም ነው›› በሚል ያስቀምጣል (ቊጥር 6)፡፡ ስለዚህ እንደ #ሥጋ ፈቃድ ሳይሆን እንደ #መንፈስ ፈቃድ መመላለስ እንደሚገባ ካሰፈረ በኋላ ‹‹ #አባ #አባት ብለን የምንጮኽበትን #የልጅነት #መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና #ለፍርሀት #የባርነትን #መንፈስ አልተቀበላችሁምና›› ይላል (ቊጥር 15)፡፡ በመቀጠል ልጆች ከሆንን ደግሞ ወራሾች ነን ይልና ‹‹ #ዐብረንም ደግሞ እንድንከበር ዐብረን #መከራ ብንቀበል #ከክርስቶስ ጋር አብረን #ወራሾች ነን›› የሚል ሐሳብ ያቀርባል፡፡ ነገር ግን #መከራው #ልንወርሰው ካለው ክብር ጋር ሲመዛዘን ‹‹ምንም እንዳይደለ አስባለሁ››፡፡ ይህ ግን ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት በሙሉ በመሆኑ ‹‹ #የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች #መገለጥ›› በመቃተት በተስፋ እየተጠባበቀ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በመቃተት ላይ ያለው ግን #ፍጥረት ብቻ ሳይሆን እኛም ጭምር መሆናችንን ያስቀምጥና ‹‹ #እንዲሁም ደግሞ #መንፈስ #ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት #እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና÷ ነገር ግን #መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት #ይማልድልናል›› ይላል፡፡ ምክንያቱንም ‹‹ #ልብንም የሚመረምረው #የመንፈስ ዐሳብ ምን እንደ ሆነ ያውቃል÷ እንደ #እግዚአብሔር ፈቃድ ስለ #ቅዱሳን #ይማልዳልና›› በማለት ያስቀምጣል፡፡ ከዚህ ቡኋላ ቀደም ሲል ያቀረበውን በዚህ ምድር የሚያገኘንን #መከራ መነሻ በማድረግ ‹‹ #እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ #አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ #ለበጎ #እንዲደረግ እናውቃለን›› በማለት ይጀምርና #እግዚአብሔር #አስቀድሞ እንደ #ወሰነን፣ እንደ #ጠራን#እንዳጸደቀን እና #እንዳከበረን አስፍሮ ‹‹ #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ማን #ይቃወመናል?›› የሚል ጥያቄ ያነሣል፡፡ እንግዲህ ከዚህ ሁሉ በኋላ ነው ‹‹ #እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? #የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው÷ #የሚኰንንስ ማን ነው?›› የሚለውን ጥያቄ በማንሣት #የኰናኙን ማንነት ለማሳየት ጥረት የሚያደርገው፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት #ኰናኙ
▶️ "የሞተ"
(ሞቱ አንድ ጊዜ ብቻ የሆነ ወደፊት የማይደገም በመሆኑ በኃላፊ ጊዜ ነው የተቀመጠው)፣

▶️ "ከሙታንም የተነሣ"
(ትንሣኤውም ቢሆን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣበት ጊዜ ብቻ የሆነ አንድ ክንውን ነውና የተነሣ አለው)፣

▶️ "በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ"
(በእግዚአብሔር ቀኝ መሆኑ ስለ ሰው ልጆች ሊታይ ነው(ዕብ 9፥24)፡፡ ይሄውም የምልጃ ሥራው አካል ነውና አሁንም ስለ እኛ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ፡፡ ስለዚህ ነው ሐዋርያው በእግዚአብሔር ቀኝ ነበረ ሳይሆን አለ ያለው)፣

▶️ "ስለ እኛ የሚማልድ" (የክርስቶስ ምልጃ ምንም እንኳ አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ በተሠራው ሥራ የተፈጸመ ስለ ሆነ የማይደጋገም ቢሆንም፣ ቀደም ሲል እንደ ተባለው አሁንም ስለ እኛ በመታየት ይቅርታን እንድናገኝ ያደርጋልና ሐዋርያው ስለ እኛ የሚማልድ በማለት አሁንም አማላጃችን መሆኑን ተናገረ።) በማለት ስለ እኛ #የሚማልድ መሆኑን በማሳየት በዚህ ምድር ላይ ያለውን #መከራ #ማሸነፍ የሚቻልበትን #ማበረታቻ ይሰጣል፡፡ ይህ ምንባብ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን #የሚከሳቸው #ማን ነው? ለሚለው #ጥያቄ #ማንም የሚል ምላሽ የሚሰጥ ሲሆን ማንም #ሊከሳቸው የማይችልበት #ምክንያት ደግሞ ስለ #እነርሱ #ሞቶ የነበረ #ሞትን #ድል አድርጎ #የተነሣው እና #በአብ ቀኝ ሆኖ #የሚያማልድላቸው #ስላለ ነው በሚል ነው የሚያስቀምጠው፡፡ #ሐዋርያው ቀደም ሲል #በክርስቶስ #ኢየሱስ ላሉት #አሁን #ኵነኔ የለባቸውም ማለቱን ማስታወሱም #ጠቃሚ ነው (ቊጥር 1)።
@ ( #ጳውሎስ "ስለ እኛ የሚማልደው" በማለት እርሱም #በክርስቶስ ኢየሱስ #የምልጃ ስራ ተጠቃሚ መሆኑን ይናገራል። አንዳንዶች #ሐዋሪያው #ጳውሎስን ጨምሮ በርካታ ሰዎችን #በምልጃ ስራ ውስጥ አሰልፈው #የክርስቶስን የምልጃ ስራ ፊት ለፊት በመቃወም ላይ ናቸው። #ሐዋሪያው በዚህ ክፍል ላይ እርሱ #አማላጅ ስለመሆኑ ሳይሆን #ስለ ኢየሱስ #አማላጅነት እና እርሱም #በኢየሱስ #ምልጃ ተጠቃሚ ስለ መሆኑ ነው የሚያስተምረው። #መጽሀፉ እንደሚለው ደግሞ #ኢየሱስ የእኛ ብቻ ሳይሆን #የቅዱስ ጳውሎስም #አማላጅ ነው። ስለ ሌሎች #ያማልዳል የሚባለው #ጳውሎስ #በክርስቶስ ምልጃ ተጠቃሚ እንደሆነ የገለጸውን መመልከት ሁላችንም #አማላጅ #እርሱ ብቻ ወደ ሆነው ወደ #ክርስቶስ እንድንጠጋ ያበረታታል።)

#በመቀጠልም ስለ እኛ #ከሞተው#ሞትን ድል አድርጎ #ከተነሣው#በእግዚአብሔር ቀኝ ካለው እና #ስለ እኛ #ከሚያማልደው ‹‹ #ከክርስቶስ #ፍቅር ማን ይለየናል? #መከራ÷ ወይስ #ጭንቀት÷ ወይስ #ስደት÷ ወይስ #ራብ÷ ወይስ #ራቁትነት÷ ወይስ #ፍርሀት÷ ወይስ #ሰይፍ ነውን?›› ሲል ይጠይቃል፡፡ በእርግጥም ከዚህ #ጌታ ምንም የሚለየን የለም፡፡ ‹‹ #ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ #እንገደላለን÷ #እንደሚታረዱ #በጎች ተቈጠርን ተብሎ›› ተጽፏልና፡፡ ‹‹በዚህ ሁሉ ግን #በወደደን [በአማላጃችን] #በእርሱ #ከአሸናፊዎች እንበልጣለን፡፡ #ሞት ቢሆን÷ #ሕይወትም ቢሆን÷ #መላእክትም ቢሆኑ÷ #ግዛትም ቢሆን÷ #ያለውም ቢሆን÷ #የሚመጣውም ቢሆን÷ #ኀይላትም ቢሆኑ÷ #ከፍታም ቢሆን÷ #ዝቅታም ቢሆን÷ #ልዩ ፍጥረትም ቢሆን #በክርስቶስ ኢየሱስ #በጌታችን ካለ #ከእግዚአብሔር #ፍቅር ሊለየን #እንዳይችል ተረድቼአለሁ›› በማለት #ምዕራፉ ያበቃል፡፡ #በዚህ ምዕራፍ ውስጥ #አሁን #ኵነኔ #የለብንም በማለት የጀመረው #ሐዋርያው #ክርስቲያኖች ስለሚያጋጥማቸው ነገር #እየመከረና #እያበረታታ ሁሉን #በጽናት #ማሸነፍ እንዳለባቸው ሲናገር፣ ‹‹ #እግዚአብሔር #የመረጣቸውን ማን #ይከሳቸዋል? #የሚያጸድቅ #እግዚአብሔር ነው÷ #የሚኰንንስ ማን ነው?›› ለሚሉት #ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ‹‹ #ስለ እኛ የሚማልደው #ክርስቶስ #ኢየሱስ›› መሆኑን ነገረን፡፡ ለዚህስ ሳይሆን ይቀራል #በአንድምታው ላይ ‹‹ #እሱ #ቢያጸድቅ ማን #ይኰንነናል፡፡ #ኢየሱስ ክርስቶስ #ሞተ #ከሙታንም #ተለይቶ #ተነሣ፡፡ #በአብ #ዕሪና(እኩል፣ መተካከል) #ይኖራል ስለ እኛ #ይከራከራል፡፡ #መከራከርስ የለም #ስለ እኛ #በዕለተ #ዐርብ #ባደረገው #ተልእኮ ፍጹም #ዋጋችንን #የምናገኝ ስለ ሆነ›› እንደ ሆነ የሰፈረው????
📖/፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሀፍ ንባቡና ትርጓሜው (አ.አ፣ ግንቦት 1988) ገጽ 70።
📖/፤ መሐሪ ትርፌ (ሊቀ ሊቃውንት)፣ የቅዱስ ጳውሎስ መጽሀፍ ንባቡ ከነትርጓሜው (አ.አ፤ ጥቅምት 23 1948) ገጽ 100።

#እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል/ዩሀ 8፥32/

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
Photo


#ስለዚህም ይህ " #መናፍቅ #የጨመሩት ነው" የሚለው ንግግር ሆን ብሎ ሰውን ለማሳሳት #የተፈጠረ መላምት ነው ከማለት ያለፈ ሊባል የሚቻለው ሌላ ነገር የለም። ይህ ራሱ #የአንዳንዶች #የማታለያ #ዘዴ ብቻ ነው እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቃሉ #እውነት እንደሆነ #ከጥንትም እንደነበረ ራሳቸውም ማመናቸው ተራጋግጧል።
ለምሳሌ፦
#ማኅበረ ቅዱሳን #ለተሐድሶ መልስ እሰጥበታለሁ ብሎ በለቀቀው ድምፅ ወምስል (ቪሲዲ) ላይ " #ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ" ይህን ጥቅስ በተመለከተ ‹‹ #ስለ እኛ #የሚማልደው የሚለው ቃሉ አለ፤ #ከጥንቱም #ከግሪኩ አለ›› የሚል #አስተያየታቸውን መስጠታቸውን መመልከት ይቻላል፡፡
(ማኅበረ ቅዱሳን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እናድሳለን ብለው የተነሡ ፕሮቴስታንቶች በሚያነሧቸው ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መልስ 2ኛው ድምፅ ወምስል፣ (መስከረም 2010)፣ 8፡11-8፡15 ደቂቃ፡፡)

ዞሮ ዞሮ ይህም የሆነው #እውነትን ደብቆ #መቀመጥ ስለማይቻል ብቻ ነው። ከዚህም በተጨማሪ #አባቶቼ እያሉ የሚጠሯቸው ፣ #መታሰቢያም የሰሩላቸው #አባቶች ይህን ቃል የተረዱት የዛሬዎቹ አንዳንድ መምህር ተብዬዎች ከሚያስቡት በተቃራኒ ነው።
@ ለምሳሌ፦
#ዮሐንስ አፈወርቅን ብንመለከት #የሮሜ መልእክትን በተረጎመበት
/" #ድርሳን 15" ይህን ቃል #እንደወረደ ተጠቅሞታል።
እንዲህ ብሏል ፦
<< #ቅዱስ ጳውሎስ " #ስለ እኛ #የሚማልደው"ብሎ #ለሥጋ እንደሚገባ አድርጎ የተናገረው #ፍቅሩን #ይገልጽ ዘንድ #በታላቅ #ትህትና የገለጸው ነው>>
ብሎ ጽፏል።
#አስተውሉ #ዮሐንስ #አፈወርቅ #የጳውሎስ ጹሕፍ ምን እንደነበረ
#ሲገልጽ እነመለከታለን።
#ጳውሎስ " #የሚማልደው"ብሎ እንደጻፈ ይህም የክርስቶስን #ትሕትና እና #በሥጋው ወይም #በሰውነቱ #አንጻር #የተነገረ እነደሆነ እና #ጌታ ለእኛ ያለውን #ፍቅር #ለሚያስረዳት የተጻፈ #መሆኑን ገልጿል።
አስተውሉ!!
#ዮሐንስ አፈወርቅ #መናፍቅ ነበር እንዴ? ነው ወይስ
#የመናፍቃንን #መጽሐፍ ቅዱስ
ነው የተረጎመው? ነው ወይስ
#እናንተ #አባታችን ከምትሉት #ዮሐንስ አፈወርቅ #ትበልጣላችሁ? ነው ወይስ
#ተሳስቶ ነበር? ምንድን ነው #የምትመልሱት?
*
#ይህም ብቻ አይደለም የክርስቶስ #አማላጅነት #ከአብ #ያንሳል ማለት እንዳልሆነ
፣እኛን ለመርዳት አቅም ስለሌለው #መለመን አስፈልጎት እንዳልሆነ ነገር ግን
ለእኛ ያለውን #ፍቅር ለማሳየት እንደሆነ ገልጿል።
#ይህን ቢገልጽም #የጳውሎስን
#ቃል #መናፍቃን #የጨመሩት ነው አላለም።
ነገር ግን ከጳውሎስ #የሰማውን ቃል #እርሱም ተቀበሎ እየደጋገመ ይናገረዋል ።
ለምሳሌ ፦

<< #ክርስቶስ አሁን #በክብሩ #የሚታይ ቢሆንም #ርኅራኄውን ከእኛ #አላራቀም #ስለእኛ
#ይማልዳል #እንጅ>>


<< #እንግዲህ #መንፈስቅዱስ ራሱ #በማይነገር #መቃተት #የሚማልድልን ከሆነ #ኢየሱስም #ሞቶ #የሚያማልደን ከሆነ #አብም #ለአንተ ሲባል #ለልጁ #ካልራራለት #አንተን #ከመረጠህ #ካጸደቀህ ከዚህ ሌላ በምን #ትፈራለህ?>>


<< #እግዚአብሔር #ዘውዱን አቀዳጅቶናል። #የሚኮንነንስ #ማነው? #ክርስቶስ #ሞቶልናል #መሞት ብቻ አይደለም ከዚህም በኋላ #ለእኛ #ስለሚማልድ ማን
#ይኮንነናል? >>
📖/፤ ሐመረ መጽሄት ሐምሌ 2007 ገጽ 10
በማለት ያብራራዋል።
#ለመሆኑ > #ዮሐንስ #አፈወርቅ< እንዲህ እየገለጸው እያለ
#መናፍቃን #የጨመሩት ነው #የምትሉት ከየት አምጥታቹ ነው? እናንተ #ሰዎች ሆይ #ከስህተታችሁ ታረሙ።
#ይህ " #ዮሐንስ #አፈወርቅ" ዕብራውያን 7:25ን በተረጎመበት ድርሳን 13 ላይ
የሮሜን መልእክት ለማስረጃ ጠቅሶታል።
ሮሜ8:34 ላይ የተጻፈውና ዕብ7:25 ላይ የተጻፈው ቃል #ተመሳሳይ እንደሆነ ያስረዳል። ይህ ዮሐንስ አፈወርቅ
#የክርስቶስን #አማላጅነት #ከፍቅር #አንጻር ይመለከተዋል ለምሳሌ፦
ዮሐ17:9-21
ያለውን #የጌታን #ምልጃ እንዲህ ገልጾታል ፦
*
<< "I pray not that You should take them out of the world, but
that You should keep them from the evil."
Again He simplifies His language; again He renders it more
clear; which is the act of one showing, by making entreaty
for them with exactness, nothing else but this, that He has a
very tender care for them. Yet He Himself had told them,
that the Father would do all things whatsoever they should
ask. How then does He here pray for them? As I said, for
no other purpose than to show His love .>>
በማለት የጸለየው የፍቅር መገለጫ መሆኑን በድርሳን 82 ገልጾታል ።
ራሱን ያለምስክር የማይተው ጌታ በእነዚህ ሰዎች ሞስክር አአስቀምጧል ።

እንግዲህ መጀመሪያ #በግሪክ የጻፈው #ሐዋርያ ስለእኛ #የሚማልደው ካለ አባቶቻችንም ይህንን #እውነት ካጸኑልን ታድያ ይህንን #በመንፈስ ቅዱስ በተሰጠ #ሐዋርያዊ ስልጣን የተጻፈን ቃል #የመለወጥ ስልጣን ያለው አለን? #ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን #እንመን? #ወይስ #እነርሱን?
አስቡበት!!

#ይህም ብቻ ሳይሆን ‹ #ስለ እኛ #ይፈርዳል› ተብሎ የተተረጐመው ቃል #ስሕተት የሆነው ንባቡ በመተርጎሙ ብቻ ሳይሆን፤ #በሕገ #ሰዋስው መሠረት ሲታይ ሐረጉ #በዐረፍተ ነገሩ ውስጥ እንዲገልጽ #የተፈለገውን ሐሳብ ስለማይገልጽና ሌላ #ትርጕም ስለሚሰጥም #ጭምር ነው እንጂ፡፡ በዐማርኛ ሰዋስው ‹ #ስለ እኛ ይፈርዳል› የሚል ንባብ " #ለእኛ ይፈርዳል› ወይም " #በእኛ ይፈርዳል" የሚል #ትርጕም ሊሰጥ አይችልም፡፡ የሚሰጠው #ፍቺ በእኛ ምትክ፣ #እኛን #ወክሎ #ይፈርዳል የሚል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ቃሉን የለወጡት ሰዎች ቃሉ እንዲናገርላቸው የፈለጉትን ‹ #ለእኛ ይፈርዳል› ወይም " #በእኛ ይፈርዳል" የሚለውን #ሐሳብ አይጠራላቸውም፡፡ እንዲያውም ያልጠበቁትን #ትርጕም ይሰጥባቸዋል፡፡ የተፈለገውን #ትርጕም ይሰጥ ዘንድ ‹ #ስለ› የሚለው መስተዋድድ #ይፈርዳል ከሚለው ግስ ጋር ሳይሆን #ይማልዳል ወይም #ይከራከራል ከሚለው #ግሥ ጋር ነው ሊሄድ የሚችለው››፡፡

ይቀጥላል..(ሮሜ 8፥34)
@gedlatnadersanat @teeod