#ሁቱትሲ
፡
፡
#በኢማኪዩሌ_ኢሊባጊዛ_እና_ስቲቭ #ኤርዊን
፡
፡#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች፡
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ቀዳሜ_ቃል
ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ከስቲቭ ኤርዊን ጋር በመተባበር የጻፈችው #ሁቱትሲ የተሰኘው መጽሐፍ ምናልባት ስለ ሩዋንዳ ከተጻፉት መጻሕፍትም ሆነ ከታዩት ፊልሞች በላይ የፍጅቱን አሰቃቂነትና ዘግናኝነት ገላጭ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፉ ከሰሚ ሰሚ የወረደ ታሪክ ሳይሆን እጅግ ከሚዋደዱ ከስድስት ቤተሰብ አባላት ከግድያው የተረፈችው አንዲት ቱትሲ ወጣት ከአንድ ቁምሣጥን በማይበልጥ መጸዳጃ ቤት ከሰባት ቱትሲ ጓደኞቿ ጋር ከአሁን አሁን ተገደልኩ እያለች እየተጨነቀች የሃይማኖት ጽናቷ እንዴት ለሦስት ወር በሕያውነት እንዳኖራትና በኋላም እንዴት ነጻ ወጥታ ወልዳ ለመሳም የበቃች መሆኗን የሚተርክ ታሪክ ነው፡፡ የሩዋንዳ የዘር ፍጅት ተዋንያንን ፍርድ ቤት እንዳቀርብ በተባበሩት መንግስታት በከፍተኛ የሕግ አማካሪነት ተቀጥሬ በሠራሁበት ጊዜ ከሰማኋቸው በላይ ልብን ሰቅዞ የሚይዝና አእምሮን የሚያናውጥ ታሪክ ይኖራል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ መጽሐፍ አጋጥሞኛል፡፡
ስሜታዊነት አይነካኝም፣ መንፈሴ በሚያየውና በሚሰማው የማይረበሽ ጠንካራ ሰው ነኝ ባይ ይህንን መጽሐፍ በሚያነብበት ጊዜ ከአንዴም ሁለቴ ዓይኖቹ በእንባ ችፍ ችፍ ማለታቸው አይቀርም፡፡
የኢማኪዩሌ ታሪክ ምንጩ ወይንም የስቃይዋ ምክንያት የተወሳሰበ አይደለም፡፡ መንስኤው ርህራሄ የሚወልደውን የሰብአዊ ስሜትን ደምስሶ ከጥላቻ በላይ ጥላቻ ወልዶ ሰውን ከአውሬነት በታች የሚያውለው የዘር ጥላቻ ነው፡፡
የዘር ጠላቻ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር ለሌላው ሰብዓዊ ፍጡር ሊኖረው የሚገባውን ሐዘኔታና ርህራሄ ከሰው ልብ ፈልቅቆ አውጥቶ ከአውሬ በባሰ ጭካኔ ይተካዋል፡፡ በሩዋንዳው የዘር ፍጅት የተፈጸመውን አራዊት ከሚያደርጉት ጋር ማወዳደር የአራዊትን ስም ማጥፋት ይሆናል፡፡ የትኛው አውሬ ነው ሕጻናትን ከታትፎ እንደ ጌሾ በሙቀጫ የሚወቅጠው? የትኛው አውሬ ነው በኢማኪዩሌ ወንድም ላይ እንደተፈጸመው የሰውን አካላት ቆራርጦ ክምር ላይ የሚጥል? የትኛው አውሬ ነው የሰውን ጭንቅላት በገጀራ ለሁለት ሰንጥቆ ሰውዬውን በዝግታ እንዲሞት የሚያደርገው? የትኛው አውሬ ነው የአምስት ልጆችን እናት በልጆቿና በባሏ ፊት ደፍሮ ፊቷ አምስቱንም ልጆቿንና ባሏን አንድ በአንድ የሚከትፈው? ከአክራሪ ሁቱዎች በስተቀር የትኛውም አውሬ አያደርገውም፡፡
የሩዋንዳ የዘር ፍጅት የሰው ልጅ ጭካኔ ልክ የታየበት ነው፡፡ ተመሳሳይ ፍጅትና ጭካኔ የተፈጸመባቸው የናዚዎችና የአርመኖች እልቂቶች እንደሩዋንዳው መንስኤአቸው የዘር ጥላቻ ነበር፡፡
ኢማኪዩሌ በመጽሐፏ የጠቀሰችው የዘር ፍጅቱ ቀስቃሽና ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ቲዩኔስት ባጎስራ ፍርድ ቤት አቅርቤው ዳኞቹ ክሱን አንብበውለት ጥፋተኛ ነህ
አይደለህም ብለው ሲጠይቁት ፈገግ እያለ ‹‹ጥፋተኛ አይደለሁም›› ሲል ፈገግታው እንደ ጦር ይዋጋ ነበር፡፡
መጽሐፉ ከእንግሊዝኛ የተተረጎመ ሲሆን፤ ምናልባትም የአማርኛው ትርጉም ድርጊቶቹን ከእንግሊዝኛው በተሻለ ይገልጻቸዋል ማለት ይቻላል፡፡ ተርጓሚው የሥነጽሑፍ ምሁር እንደመሆናቸው መጠን አገላለጹ ከኢማኪዩሌ በልጦ ቢገኝ አይገርምም፡፡ የቃላቱ ገላጭነት፣ የአረፍተ ነገሮቹ አሰካክ፣ የቋንቋው አወራረድና በጠቅላላው የአማርኛው ውበት ከታሪኩ መሳጭነት ጋር ሆኖ መጽሐፉን ማንበብ ከተጀመረ መልሶ ማስቀመጥ አስቸጋሪ ነው፡፡
ይህ መጽሐፍ የብሔር ጥላቻ የሚፈጥሩ ፖሊሲዎችን ለሚቀርጹና በብሔረሰብ ስም ህዝብን ከፋፍለው ጥላቻ ለሚያስፋፉ ሰዎችም ሆኑ መዋቅርት የማስጠንቀቂያ ደወል ነው፡፡ መጽሐፉ ጥላቻ የሚያስከትለውን ሰቆቃ በግልጽ ስለሚያሳይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲያነበው በአጽንኦት ስማጠን በዓይኔ በብረቱ ካየሁት ተነሥቼ ነው፡፡
ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለ ማርያም
በተባበሩት መንግስታት የቀድሞ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት ከፍተኛ የሕግ አማካሪ
#መግቢያ
ኢማኪዩሌ እባላለሁ
ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰማኋቸው፡፡
እኔ በግንቡ በአንደኛው በኩል ስሆን እነሱ ደግሞ በሌላኛው አቅጣጫ ናቸው፤ አንድ ጋት የማይሞላ ውፍረት ያለው ጭቃና ዕንጨት ብቻ ይለያየናል፡፡ ንግግራቸው ጭካኔ የሚንጸባረቅበትና ቆርጠው መነሳታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
‹‹እዚህ ነች… እዚህ የሆነ ስፍራ እንዳለች እናውቃለን፡፡ …. ፈልጓት-ፈልጓት ኢማኪዩሌን፡፡››
አካባቢው በሁካታ ተሞላ፡፡ ብዙ ገዳዮች መጥተዋል፡፡ በአእምሮዬ ይታዩኛል - ሁልጊዜ በፍቅርና በደግነት ሰላምታ ይሰጡኝ የነበሩ የቀድሞ ወዳጆቼና ጎረቤቶቼ በቤቱ ውስጥ ጦርና ገጀራ ይዘው ስሜን እየጠሩ ይዘዋወራሉ፡፡
‹‹399 በረሮዎችን ገድያለሁ›› ይላል አንደኛው ገዳይ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ 400 ታደርግልኛለች፡፡ ይህን ያህል ከገደልኩ ምን እፈልጋለሁ!››
በትንሿ ምስጢራዊ መታጠቢያ ቤታችን ጥጋት አንድስ እንኳን የሰውነቴን ክፍል ሳላላውስ ተሸሽጌያለሁ፡፡ እንደኔው ሕይወታቸውን ለማትረፍ እንደተደበቁት ሌሎች ሰባት ሴቶች ሁሉ ገዳዮቹ ስተነፍስ እንዳይሰሙኝ ትንፋሼን ውጫለሁ፡፡ ድምጻቸው የሠራ አከላቴን ገማመሰው፡፡ በከሰል ፍም ላይ እንደተኛሁ፣ እሳትም ላይ እንደተጣልኩ ተሰማኝ፡፡ መላ ሰውነቴ የሕመም ውርጅብኝ ወረደበት፡፡ ሺህ የማይታዩ መርፌዎች ተቸከቸኩብኝ፡፡ ፍርሃት እንደዚህ የሚያርበደብድ ስጋዊ ሥቃይ ያስከትላል ብዬ አስቤ አላውቅም፡፡
ለመዋጥ ሞከርኩ፤ ጉሮሮዬ ግን ተዘግቷል፡፡ ምራቅ አልነበረኝም፤ አፌም እንደ ኩበት ደርቋል፡፡ ዓይኖቼን ጨፈንኳቸው፤ ራሴንም ለመደበቅ ሞከርኩ፤ ንግግራቸው ግን እየጎላ መጣ፡፡ ምንም ዓይነት ምኅረት እንደማያደርጉልኝ አውቃለሁ፤ በአእምሮዬም አንድ ሐሳብ ያስተጋባ ጀመር - ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ
ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል…
ገዳዮቹ በራፉ ላይ አሉ፤ በማንኛዋም አፍታ እንደሚያገኙኝ አውቃለሁ፡፡ ገጀራው ቆዳዬን አልፎ ሲገባና አጥንቴ ድረስ ሲቆራርጠኝ የሚሰማኝ ስሜት ምን እንደሚመስል አሰብኩት፡፡ ወንድሞቼና ወላጆቼም ትዝ አሉኝ፤ ሞተው ወይንም በሕይወት እየኖሩ እንደሆነ፣ በገነት ከአፍታ በኋላ እንገናኝም እንደሆነ አለምኩ፡፡
እጆቼን እርስ በርሳቸው አጣመርኳቸው፤ የአባቴን መቁጠሪያም ጥብቅ አድርጌ ያዝኩ፤ በለሆሳስም መጸለይ ጀመርኩ - እባክህ እግዚአብሔር ሆይ፣ እባክህ እርዳኝ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ እንድሞት አታድርገኝ፣ እንደዚህ አይሁን፡፡ እነዚህ ገዳዮች እንዲያገኙኝ አታድርግ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስህ ከጠየቅን እንደሚሰጠን ትነግረናለህ… እንግዲህ ጌታዬ እየጠየኩህ ነው፡፡ ወይ በለኝ፡፡ እባክህን እነዚህን ገዳዮች ወዲያ እንዲሄዱ አድርጋቸው፡፡ ኧረ በዚህ መታጠቢያ ቤት እንድሞት አታድርገኝ፡፡ እባክህ፣ እግዚአብሔር፣ እባክህ፣ እባክህ፣ እባክህ አድነኝ፡፡
ገዳዮቹ ከቤቱ ወጥተው ሄዱ፡፡ እኛም እንደገና መተንፈስ ጀመርን፡፡ ሄደዋል፤ ሆኖም ግን በቀጣዮቹ ሦስት ወራት ውስጥ ብዙ ጊዜ ይመላለሳሉ፡፡ ሕይወቴን እግዚአብሔር እንዳተረፋት አምናለሁ፤ ሆኖም ቁምሣጥን በምታክል መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ከሰባት ሌሎች ሰዎች ጋር በፍርሃት እየተርበደበድኩ ባሳለፍኳቸው 91 ቀናት መትረፍ ከመዳን በጣም የተለየ አንደሆነ እማራለሁ… ይህ ትምህርትም ለዘለቄታው ለውጦኛል፡፡ ይህ ትምህርት በጅምላ ጭፍጨፋ ውስጥ የሚጠሉና
፡
፡
#በኢማኪዩሌ_ኢሊባጊዛ_እና_ስቲቭ #ኤርዊን
፡
፡#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች፡
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ቀዳሜ_ቃል
ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ከስቲቭ ኤርዊን ጋር በመተባበር የጻፈችው #ሁቱትሲ የተሰኘው መጽሐፍ ምናልባት ስለ ሩዋንዳ ከተጻፉት መጻሕፍትም ሆነ ከታዩት ፊልሞች በላይ የፍጅቱን አሰቃቂነትና ዘግናኝነት ገላጭ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፉ ከሰሚ ሰሚ የወረደ ታሪክ ሳይሆን እጅግ ከሚዋደዱ ከስድስት ቤተሰብ አባላት ከግድያው የተረፈችው አንዲት ቱትሲ ወጣት ከአንድ ቁምሣጥን በማይበልጥ መጸዳጃ ቤት ከሰባት ቱትሲ ጓደኞቿ ጋር ከአሁን አሁን ተገደልኩ እያለች እየተጨነቀች የሃይማኖት ጽናቷ እንዴት ለሦስት ወር በሕያውነት እንዳኖራትና በኋላም እንዴት ነጻ ወጥታ ወልዳ ለመሳም የበቃች መሆኗን የሚተርክ ታሪክ ነው፡፡ የሩዋንዳ የዘር ፍጅት ተዋንያንን ፍርድ ቤት እንዳቀርብ በተባበሩት መንግስታት በከፍተኛ የሕግ አማካሪነት ተቀጥሬ በሠራሁበት ጊዜ ከሰማኋቸው በላይ ልብን ሰቅዞ የሚይዝና አእምሮን የሚያናውጥ ታሪክ ይኖራል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ መጽሐፍ አጋጥሞኛል፡፡
ስሜታዊነት አይነካኝም፣ መንፈሴ በሚያየውና በሚሰማው የማይረበሽ ጠንካራ ሰው ነኝ ባይ ይህንን መጽሐፍ በሚያነብበት ጊዜ ከአንዴም ሁለቴ ዓይኖቹ በእንባ ችፍ ችፍ ማለታቸው አይቀርም፡፡
የኢማኪዩሌ ታሪክ ምንጩ ወይንም የስቃይዋ ምክንያት የተወሳሰበ አይደለም፡፡ መንስኤው ርህራሄ የሚወልደውን የሰብአዊ ስሜትን ደምስሶ ከጥላቻ በላይ ጥላቻ ወልዶ ሰውን ከአውሬነት በታች የሚያውለው የዘር ጥላቻ ነው፡፡
የዘር ጠላቻ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር ለሌላው ሰብዓዊ ፍጡር ሊኖረው የሚገባውን ሐዘኔታና ርህራሄ ከሰው ልብ ፈልቅቆ አውጥቶ ከአውሬ በባሰ ጭካኔ ይተካዋል፡፡ በሩዋንዳው የዘር ፍጅት የተፈጸመውን አራዊት ከሚያደርጉት ጋር ማወዳደር የአራዊትን ስም ማጥፋት ይሆናል፡፡ የትኛው አውሬ ነው ሕጻናትን ከታትፎ እንደ ጌሾ በሙቀጫ የሚወቅጠው? የትኛው አውሬ ነው በኢማኪዩሌ ወንድም ላይ እንደተፈጸመው የሰውን አካላት ቆራርጦ ክምር ላይ የሚጥል? የትኛው አውሬ ነው የሰውን ጭንቅላት በገጀራ ለሁለት ሰንጥቆ ሰውዬውን በዝግታ እንዲሞት የሚያደርገው? የትኛው አውሬ ነው የአምስት ልጆችን እናት በልጆቿና በባሏ ፊት ደፍሮ ፊቷ አምስቱንም ልጆቿንና ባሏን አንድ በአንድ የሚከትፈው? ከአክራሪ ሁቱዎች በስተቀር የትኛውም አውሬ አያደርገውም፡፡
የሩዋንዳ የዘር ፍጅት የሰው ልጅ ጭካኔ ልክ የታየበት ነው፡፡ ተመሳሳይ ፍጅትና ጭካኔ የተፈጸመባቸው የናዚዎችና የአርመኖች እልቂቶች እንደሩዋንዳው መንስኤአቸው የዘር ጥላቻ ነበር፡፡
ኢማኪዩሌ በመጽሐፏ የጠቀሰችው የዘር ፍጅቱ ቀስቃሽና ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ቲዩኔስት ባጎስራ ፍርድ ቤት አቅርቤው ዳኞቹ ክሱን አንብበውለት ጥፋተኛ ነህ
አይደለህም ብለው ሲጠይቁት ፈገግ እያለ ‹‹ጥፋተኛ አይደለሁም›› ሲል ፈገግታው እንደ ጦር ይዋጋ ነበር፡፡
መጽሐፉ ከእንግሊዝኛ የተተረጎመ ሲሆን፤ ምናልባትም የአማርኛው ትርጉም ድርጊቶቹን ከእንግሊዝኛው በተሻለ ይገልጻቸዋል ማለት ይቻላል፡፡ ተርጓሚው የሥነጽሑፍ ምሁር እንደመሆናቸው መጠን አገላለጹ ከኢማኪዩሌ በልጦ ቢገኝ አይገርምም፡፡ የቃላቱ ገላጭነት፣ የአረፍተ ነገሮቹ አሰካክ፣ የቋንቋው አወራረድና በጠቅላላው የአማርኛው ውበት ከታሪኩ መሳጭነት ጋር ሆኖ መጽሐፉን ማንበብ ከተጀመረ መልሶ ማስቀመጥ አስቸጋሪ ነው፡፡
ይህ መጽሐፍ የብሔር ጥላቻ የሚፈጥሩ ፖሊሲዎችን ለሚቀርጹና በብሔረሰብ ስም ህዝብን ከፋፍለው ጥላቻ ለሚያስፋፉ ሰዎችም ሆኑ መዋቅርት የማስጠንቀቂያ ደወል ነው፡፡ መጽሐፉ ጥላቻ የሚያስከትለውን ሰቆቃ በግልጽ ስለሚያሳይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲያነበው በአጽንኦት ስማጠን በዓይኔ በብረቱ ካየሁት ተነሥቼ ነው፡፡
ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለ ማርያም
በተባበሩት መንግስታት የቀድሞ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት ከፍተኛ የሕግ አማካሪ
#መግቢያ
ኢማኪዩሌ እባላለሁ
ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰማኋቸው፡፡
እኔ በግንቡ በአንደኛው በኩል ስሆን እነሱ ደግሞ በሌላኛው አቅጣጫ ናቸው፤ አንድ ጋት የማይሞላ ውፍረት ያለው ጭቃና ዕንጨት ብቻ ይለያየናል፡፡ ንግግራቸው ጭካኔ የሚንጸባረቅበትና ቆርጠው መነሳታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
‹‹እዚህ ነች… እዚህ የሆነ ስፍራ እንዳለች እናውቃለን፡፡ …. ፈልጓት-ፈልጓት ኢማኪዩሌን፡፡››
አካባቢው በሁካታ ተሞላ፡፡ ብዙ ገዳዮች መጥተዋል፡፡ በአእምሮዬ ይታዩኛል - ሁልጊዜ በፍቅርና በደግነት ሰላምታ ይሰጡኝ የነበሩ የቀድሞ ወዳጆቼና ጎረቤቶቼ በቤቱ ውስጥ ጦርና ገጀራ ይዘው ስሜን እየጠሩ ይዘዋወራሉ፡፡
‹‹399 በረሮዎችን ገድያለሁ›› ይላል አንደኛው ገዳይ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ 400 ታደርግልኛለች፡፡ ይህን ያህል ከገደልኩ ምን እፈልጋለሁ!››
በትንሿ ምስጢራዊ መታጠቢያ ቤታችን ጥጋት አንድስ እንኳን የሰውነቴን ክፍል ሳላላውስ ተሸሽጌያለሁ፡፡ እንደኔው ሕይወታቸውን ለማትረፍ እንደተደበቁት ሌሎች ሰባት ሴቶች ሁሉ ገዳዮቹ ስተነፍስ እንዳይሰሙኝ ትንፋሼን ውጫለሁ፡፡ ድምጻቸው የሠራ አከላቴን ገማመሰው፡፡ በከሰል ፍም ላይ እንደተኛሁ፣ እሳትም ላይ እንደተጣልኩ ተሰማኝ፡፡ መላ ሰውነቴ የሕመም ውርጅብኝ ወረደበት፡፡ ሺህ የማይታዩ መርፌዎች ተቸከቸኩብኝ፡፡ ፍርሃት እንደዚህ የሚያርበደብድ ስጋዊ ሥቃይ ያስከትላል ብዬ አስቤ አላውቅም፡፡
ለመዋጥ ሞከርኩ፤ ጉሮሮዬ ግን ተዘግቷል፡፡ ምራቅ አልነበረኝም፤ አፌም እንደ ኩበት ደርቋል፡፡ ዓይኖቼን ጨፈንኳቸው፤ ራሴንም ለመደበቅ ሞከርኩ፤ ንግግራቸው ግን እየጎላ መጣ፡፡ ምንም ዓይነት ምኅረት እንደማያደርጉልኝ አውቃለሁ፤ በአእምሮዬም አንድ ሐሳብ ያስተጋባ ጀመር - ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ
ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል…
ገዳዮቹ በራፉ ላይ አሉ፤ በማንኛዋም አፍታ እንደሚያገኙኝ አውቃለሁ፡፡ ገጀራው ቆዳዬን አልፎ ሲገባና አጥንቴ ድረስ ሲቆራርጠኝ የሚሰማኝ ስሜት ምን እንደሚመስል አሰብኩት፡፡ ወንድሞቼና ወላጆቼም ትዝ አሉኝ፤ ሞተው ወይንም በሕይወት እየኖሩ እንደሆነ፣ በገነት ከአፍታ በኋላ እንገናኝም እንደሆነ አለምኩ፡፡
እጆቼን እርስ በርሳቸው አጣመርኳቸው፤ የአባቴን መቁጠሪያም ጥብቅ አድርጌ ያዝኩ፤ በለሆሳስም መጸለይ ጀመርኩ - እባክህ እግዚአብሔር ሆይ፣ እባክህ እርዳኝ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ እንድሞት አታድርገኝ፣ እንደዚህ አይሁን፡፡ እነዚህ ገዳዮች እንዲያገኙኝ አታድርግ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስህ ከጠየቅን እንደሚሰጠን ትነግረናለህ… እንግዲህ ጌታዬ እየጠየኩህ ነው፡፡ ወይ በለኝ፡፡ እባክህን እነዚህን ገዳዮች ወዲያ እንዲሄዱ አድርጋቸው፡፡ ኧረ በዚህ መታጠቢያ ቤት እንድሞት አታድርገኝ፡፡ እባክህ፣ እግዚአብሔር፣ እባክህ፣ እባክህ፣ እባክህ አድነኝ፡፡
ገዳዮቹ ከቤቱ ወጥተው ሄዱ፡፡ እኛም እንደገና መተንፈስ ጀመርን፡፡ ሄደዋል፤ ሆኖም ግን በቀጣዮቹ ሦስት ወራት ውስጥ ብዙ ጊዜ ይመላለሳሉ፡፡ ሕይወቴን እግዚአብሔር እንዳተረፋት አምናለሁ፤ ሆኖም ቁምሣጥን በምታክል መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ከሰባት ሌሎች ሰዎች ጋር በፍርሃት እየተርበደበድኩ ባሳለፍኳቸው 91 ቀናት መትረፍ ከመዳን በጣም የተለየ አንደሆነ እማራለሁ… ይህ ትምህርትም ለዘለቄታው ለውጦኛል፡፡ ይህ ትምህርት በጅምላ ጭፍጨፋ ውስጥ የሚጠሉና
👍3❤2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#በኢማኪዩሌ_ኢሊባጊዛ_እና_ስቲቭ_ኤርዊን
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ክፉ_ቀን_ዳር_ዳር_ሲል
#ምዕራፍ_አንድ
የዘላለማዊ ፀደይ ምድር
የተወለድኩት በገነት ነው፡፡ስለ ትውልድ ሀገሬ በልጅነት ዘመኔ የሚሰማኝ ይህ ነበር፡፡ሩዋንዳ በመካከለኛው አፍሪካ እንደጌጥ ጣል የተደረገች ትንሽ ሀገር ነች፡፡ በጣም ማራኪ ውበት ስላላት፣ በለምለም ሸንተረሮቿ፣ ጭጋግ በሸፈናቸው ተራሮቿ፣ በአረንጓዴ ሸለቆዎቿና በአንጸባራቂ ሐይቆቿ ተማርኮ ለምስጋና ወደ አምላክ አለማንጋጠጥ የማይታሰብ ነው፡፡ ከተራሮቿ ቁልቁል የተለያየ ዝርያ ወዳላቸው የጽድ ጫካዎቿ የሚወርደው ነፋሻ አየር በልዩ ልዩ አበቦች መዐዛ የተሞላ ነው፡፡ የአየሩም ሁኔታ ዓመቱን ሙሉ በጣም ተስማሚ በመሆኑ በ19ኛው ክፍለዘመን መጨረሻ አካባቢ ወደ ስፍራው የመጡት የጀርመን ሰፋሪዎች ሀገሪቱን ‹‹የዘላለማዊ ፀደይ ምድር›› ብለው ሰየሟት፡፡
ውድ ሀገሬን በደም ጎርፍ እንድትታጠብ ያደረጓት ለጅምላ ጭፍጨፋ መነሻ የሆኑት ርኩሳን ሃይሎች በልጅነቴ ተሰውረውብኝ ነበር፡፡ በልጅነቴ የማውቀው ነገር የከበበኝን አማላይ መልከዓምድር፣ የጎረቤቶቼን ደግነት፣ የወላጆቼንና የወንድሞቼን ጥልቅ ፍቅር ነበር፡፡ በቤታችን ዘረኝነትና ምክንያት የለሽ ጥላቻ በፍጹም አይታወቁም፡፡ ሰዎች የተለያየ ጎሳና ዘር እንዳላቸው እንኳ ግንዛቤው አልነበረኝም፤ ቱትሲና ሁቱ የሚሉትን ቃላትም ቢሆን ትምህርት ቤት እስከገባሁበት ጊዜ ድረስ አልሰማኋቸውም፡፡
በሰፈሬ ትንንሽ ልጆች ከቤት ወደ ትምህርት ቤት ብቻቸውን ጭር ባለው አሥራ ሦስት ኪሎሜትር መንገድ ሲመላለሱ ወላጆቻቸው ልጄ ይጠለፍብኛል ወይንም በማናቸውም መንገድ ይጎዳብኛል ብለው አይጨነቁም፡፡ ልጅ ሆኜ በጣም የምፈራው ነገር በጨለማ ብቻዬን መሆንን ሲሆን፤ ከዚያ በስተቀር ግን ሰዎች የሚከባበሩበት፣ የሚተሳሰቡበትና ደስተኛ ይመስለኝ በነበረ መንደር ውስጥ ከደስተኛ ቤተሰብ ጋር የምኖር በጣም ፍልቅልቅ ልጅ ነበርኩ፡፡
የተወለድኩት በምዕራብ ሩዋንዳዋ የኪቡዬ ክፍለ-ሀገር፣ በማታባ መንደር ነው፡፡ ቤታችን ከኪቩ ሐይቅ ትይዩ በሚገኝ ኮረብታ ላይ ያለ ሲሆን፤ ሐይቁም ከፊታችን እስከ ዓለም ጠርዝ የተዘረጋ ይመስላል፡፡ ጠዋት ሰማዩ ከጠራ በሐይቁ በሌላኛው ጠርዝ በጎረቤት ሀገር ዛየር፣ በአሁኑ አጠራሩ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ያሉትን ተራሮች አያለሁ፡፡ ከቤታችን ወደ ሐይቁ የሚወስደውን አስቸጋሪ ቁልቁለት መውረድ ከአስደሳች የልጅነት ትዝታዎቼ አንዱ ነው፡፡ የማለዳው ጤዛ በንጋቷ ጸሐይ ተኖ የሚያልቅበት ጊዜ ሲቃረብ ከአባቴና ከወንድሞቼ ጋር ወደ ዋና እወርዳለሁ፡፡ ውሃው ሞቃት፣ የአየሩ ቅዝቃዜ ውርር የሚያደርግና ከሐይቁ ዳርቻ ያለው የቤታችን እይታ ዘወትር አማላይ ነበር፡፡
አቀበቱና በእግራችን የምንረግጠው አሳሳች ልል አፈር ወደ ቤት የምናደርገውን የመልስ ጉዞ አስፈሪም አስደሳችም ያደርጉታል፡፡ ብዙውን ጊዜ ስለሚያንሸራትተኝ ገደል ገብቼ ሐይቁ ውስጥ እንዳልወድቅ እፈራለሁ፡፡ አባቴም ሁልጊዜ ስፈራ ስለሚያውቅ እቤት እስክንደርስ ድረስ በእጁ ይደግፈኛል፡፡ ትልቅና ጠንካራም በመሆኑ በእነዚያ ትላልቅ እጆቹ በመያዜ ደህንነት ይሰማኛል፤ እንደተወደድኩም ይገባኛል፡፡ እንደዚያ በፍቅር ጢል መደረግ ደስ ያሰኘኛል፡፡ ለዚህም ምክንያት የሆነው በተለይ አባቴ ምንም እንኳን እንደሚወደን ብናውቅም በዘልማዳዊው መንገድ የሚያምን፣ ስሜቱን ብዙውን ጊዜ አውጥቶ የማያሳይና ወንድሞቼንም ሆነ እኔን እንደሚወደን የማይነግረን በመሆኑ ነው፡፡
ከዋና ስንመለስ ቆንጆዋ እናቴ በየቀኑ ወደ ትምህርት ቤት ከመሄዳችን በፊት የምትመግበንን ትኩስ የሩዝና የፎሶሊያ ቁርስ እየሠራች በኩሽና ስትባትል እናገኛታለን፡፡ ብርታቷ እኔን ከማስደነቅ ቦዝኖ አያውቅም - እማማ ሁልጊዜ ከቤተሰባችን አባላት ሁሉ ከእንቅልፍ ለመነሳት የመጀመሪያዋና ወደ መኝታ ለመሄድ የመጨረሻዋ ነበረች፤ ቤቱን እንደሚጠበቀው ለማሠጋደድ፣ ልብሶቻችንን ለማስተካከል፣ መጻህፍታችንንና በትምህርት ቤት የሚጠበቁብንን ጉዳዮች ለማዘገጃጀትና የአባቴን የሥራ ወረቀቶች ለማደራጀት ከሁላችንም በፊት ቀድማ እየተነሣች ትለፋለች፡፡ ልብሶቻችንን ሁሉ እሷው በልካችን ትሰፋለች፣ ጸጉራችንን ትቆርጣለች፤ ቤቱንም በእጅ ሥራዎች ጌጦች ታሸበርቀዋለች፡፡ ለቁርሳችን የምትሠራው ፎሶሊያ የሚለማው እኛ ጠዋት ከመኝታችን ሳንነሳ እማማ በምትንከባከበው በጓሮ አትክልት ማሳችን ነው፡፡ እህሉን ቃኝታ ለቀን ሠራተኞቹ የእርሻ መሣሪያዎች ታከፋፍልና ላሞቻችንና ሌሎቹ እንስሶቻችን እንዲቀለቡና እንዲታጠቡ ታደርጋለች፡፡ እነዚህን የማለዳ ሥራዎቿን ከጨራረሰች በኋላ እኛን ወደ ትምህርት ቤት ትሸኝና በእግሯ ቁልቁል መንገዱን ይዛ የሙሉ ጊዜ የማስተማር ሥራዋን ለመጀመር በአቅራቢያችን ወዳለው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትሄዳለች፡፡
ወላጆቼ መምህራን ነበሩ፡፡ ድህነትንና ርሃብን ብቸኛው መመከቻም ትምህርት እንደሆነ በጽኑ ያምናሉ፡፡ በቆዳ ስፋቷ ከሞላ ጎደል ጂቡቲን የምታክለው ሩዋንዳ ከአፍሪካ ትናንሽ ሀገራት አንዷ ብትሆንም በአህጉሩ በከፍተኛ የሕዝብ ጥግግት ተጠቃሽና ከዓለምም ደሃ ሀገራት አንዷ ነች፡፡ እናቴና አባቴ ከየቤተሰቦቻቸው የመጀመሪያዎቹ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቁ ሰዎች ሲሆኑ ልጆቻቸው እነርሱ ከደረሱበትም በላይ እንድንደርስላቸው ቆርጠዋል፡፡ አባባ ጠንክሮ በመሥራትና በሕይወቱ ሙሉ በማጥናት አርዓያ ሆኖናል፡፡ በሥራ ሕይወቱ ብዙ ክብሮችንና ዕድገቶችን ያገኘ ሲሆን፤ በአጭር ጊዜም ከአንደኛ ደረጃ መምህርነት ወደ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርነት አድጓል፡፡ በኋላም በአውራጃችን ላሉት ለሁሉም የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች ዋና አስተዳዳሪ ሆኖ ተሾሟል፡፡ በሩዋንዳ እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ልዩ የሆነ መጠሪያ ስም አለው፡፡ ለእያንዳንዱ ልጅ ወላጆች ልጁ ሲወለድ እናቱ ወይንም አባቱ መጀመሪያ ባዩት ጊዜ የተሰማቸውን ስሜት የሚያንጸባርቅ ስም ይሰጡታል፡፡ ኪንያሩዋንዳ በሚባለው ያገራችን ቋንቋ የኔ ስም (ኢሊባጊዛ) ትርጉሙ ‹‹መንፈሰ-ብሩህና ግሩም ጸዳል ያላት›› ማለት ነው፡፡ ይህን ስም ያወጣልኝ አባቴ ከተወለድኩባት ቅጽበት ጀምሮ ምን ያህል እንደሚወደኝ ስሜ ሁልጊዜ ሲያስታውሰኝ ይኖራል፡፡
የአባቴ ስም ሊኦናርድ፣ የእናቴ ደግሞ ማሬ ሮዝ ሲሆን፤ እናቴን ባልንጀሮቿ ሮዝ እያሉ ይጠሯታል፡፡ በ1963 ክረምት በአንደኛዋ የአክስቴ ልጅ ቤት ወላጆቼ ወደጋራ ጓደኛቸው ሰርግ ሲሄዱ ይገናኛሉ፡፡ ሲተዋወቁ አባቴ ጸጉሩ አድጎ እንደነገሩ ስለነበር እናቴ አየት አድርጋው ከንፈሯን መጠጠችለት፡፡
‹‹ጸጉርህ እንደዚህ ሆኖ ሰርግ ልትሄድ ነው?›› በማለት በቁጭት ጠየቀችው፡፡ አባቴ ጸጉር አስተካካይ ማግኘት እንዳልቻለ ገልጾ ‹ምን ላድርገው ብለሽ ነው› በሚል ስሜት ትከሻውን ነቀነቀ፡፡ ወዲያውኑ እዚያው እናቴ መቀስ ፈልጋ አባቴን አመቺ ስፍራ አስቀመጠችና ጸጉሩን ማስተካከል ጀመረች፡፡ ጸጉር ቆረጣውን እንዳሳመረችው አይጠረጠርም - ከዚያ ጀምሮ አልተለያዩምና፡፡ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ታጋብተው አባቴ ከዚያ በኋላ እናቴ እንጂ ሌላ ማንም ሰው ጸጉሩን እንደማያስተካክለው አረጋገጠ፡፡
ወላጆቼ በማስተማር ሥራቸውና አያቴ የሰጣቸውን መሬት በማረስ (ባቄላ፣ ሙዝና ቡና እያመረቱ ይሸጡ ነበር) ከሚያገኙት ገቢ ትንሽ ገንዘብ መቆጠብ ቻሉ
፡
፡
#በኢማኪዩሌ_ኢሊባጊዛ_እና_ስቲቭ_ኤርዊን
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ክፉ_ቀን_ዳር_ዳር_ሲል
#ምዕራፍ_አንድ
የዘላለማዊ ፀደይ ምድር
የተወለድኩት በገነት ነው፡፡ስለ ትውልድ ሀገሬ በልጅነት ዘመኔ የሚሰማኝ ይህ ነበር፡፡ሩዋንዳ በመካከለኛው አፍሪካ እንደጌጥ ጣል የተደረገች ትንሽ ሀገር ነች፡፡ በጣም ማራኪ ውበት ስላላት፣ በለምለም ሸንተረሮቿ፣ ጭጋግ በሸፈናቸው ተራሮቿ፣ በአረንጓዴ ሸለቆዎቿና በአንጸባራቂ ሐይቆቿ ተማርኮ ለምስጋና ወደ አምላክ አለማንጋጠጥ የማይታሰብ ነው፡፡ ከተራሮቿ ቁልቁል የተለያየ ዝርያ ወዳላቸው የጽድ ጫካዎቿ የሚወርደው ነፋሻ አየር በልዩ ልዩ አበቦች መዐዛ የተሞላ ነው፡፡ የአየሩም ሁኔታ ዓመቱን ሙሉ በጣም ተስማሚ በመሆኑ በ19ኛው ክፍለዘመን መጨረሻ አካባቢ ወደ ስፍራው የመጡት የጀርመን ሰፋሪዎች ሀገሪቱን ‹‹የዘላለማዊ ፀደይ ምድር›› ብለው ሰየሟት፡፡
ውድ ሀገሬን በደም ጎርፍ እንድትታጠብ ያደረጓት ለጅምላ ጭፍጨፋ መነሻ የሆኑት ርኩሳን ሃይሎች በልጅነቴ ተሰውረውብኝ ነበር፡፡ በልጅነቴ የማውቀው ነገር የከበበኝን አማላይ መልከዓምድር፣ የጎረቤቶቼን ደግነት፣ የወላጆቼንና የወንድሞቼን ጥልቅ ፍቅር ነበር፡፡ በቤታችን ዘረኝነትና ምክንያት የለሽ ጥላቻ በፍጹም አይታወቁም፡፡ ሰዎች የተለያየ ጎሳና ዘር እንዳላቸው እንኳ ግንዛቤው አልነበረኝም፤ ቱትሲና ሁቱ የሚሉትን ቃላትም ቢሆን ትምህርት ቤት እስከገባሁበት ጊዜ ድረስ አልሰማኋቸውም፡፡
በሰፈሬ ትንንሽ ልጆች ከቤት ወደ ትምህርት ቤት ብቻቸውን ጭር ባለው አሥራ ሦስት ኪሎሜትር መንገድ ሲመላለሱ ወላጆቻቸው ልጄ ይጠለፍብኛል ወይንም በማናቸውም መንገድ ይጎዳብኛል ብለው አይጨነቁም፡፡ ልጅ ሆኜ በጣም የምፈራው ነገር በጨለማ ብቻዬን መሆንን ሲሆን፤ ከዚያ በስተቀር ግን ሰዎች የሚከባበሩበት፣ የሚተሳሰቡበትና ደስተኛ ይመስለኝ በነበረ መንደር ውስጥ ከደስተኛ ቤተሰብ ጋር የምኖር በጣም ፍልቅልቅ ልጅ ነበርኩ፡፡
የተወለድኩት በምዕራብ ሩዋንዳዋ የኪቡዬ ክፍለ-ሀገር፣ በማታባ መንደር ነው፡፡ ቤታችን ከኪቩ ሐይቅ ትይዩ በሚገኝ ኮረብታ ላይ ያለ ሲሆን፤ ሐይቁም ከፊታችን እስከ ዓለም ጠርዝ የተዘረጋ ይመስላል፡፡ ጠዋት ሰማዩ ከጠራ በሐይቁ በሌላኛው ጠርዝ በጎረቤት ሀገር ዛየር፣ በአሁኑ አጠራሩ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ያሉትን ተራሮች አያለሁ፡፡ ከቤታችን ወደ ሐይቁ የሚወስደውን አስቸጋሪ ቁልቁለት መውረድ ከአስደሳች የልጅነት ትዝታዎቼ አንዱ ነው፡፡ የማለዳው ጤዛ በንጋቷ ጸሐይ ተኖ የሚያልቅበት ጊዜ ሲቃረብ ከአባቴና ከወንድሞቼ ጋር ወደ ዋና እወርዳለሁ፡፡ ውሃው ሞቃት፣ የአየሩ ቅዝቃዜ ውርር የሚያደርግና ከሐይቁ ዳርቻ ያለው የቤታችን እይታ ዘወትር አማላይ ነበር፡፡
አቀበቱና በእግራችን የምንረግጠው አሳሳች ልል አፈር ወደ ቤት የምናደርገውን የመልስ ጉዞ አስፈሪም አስደሳችም ያደርጉታል፡፡ ብዙውን ጊዜ ስለሚያንሸራትተኝ ገደል ገብቼ ሐይቁ ውስጥ እንዳልወድቅ እፈራለሁ፡፡ አባቴም ሁልጊዜ ስፈራ ስለሚያውቅ እቤት እስክንደርስ ድረስ በእጁ ይደግፈኛል፡፡ ትልቅና ጠንካራም በመሆኑ በእነዚያ ትላልቅ እጆቹ በመያዜ ደህንነት ይሰማኛል፤ እንደተወደድኩም ይገባኛል፡፡ እንደዚያ በፍቅር ጢል መደረግ ደስ ያሰኘኛል፡፡ ለዚህም ምክንያት የሆነው በተለይ አባቴ ምንም እንኳን እንደሚወደን ብናውቅም በዘልማዳዊው መንገድ የሚያምን፣ ስሜቱን ብዙውን ጊዜ አውጥቶ የማያሳይና ወንድሞቼንም ሆነ እኔን እንደሚወደን የማይነግረን በመሆኑ ነው፡፡
ከዋና ስንመለስ ቆንጆዋ እናቴ በየቀኑ ወደ ትምህርት ቤት ከመሄዳችን በፊት የምትመግበንን ትኩስ የሩዝና የፎሶሊያ ቁርስ እየሠራች በኩሽና ስትባትል እናገኛታለን፡፡ ብርታቷ እኔን ከማስደነቅ ቦዝኖ አያውቅም - እማማ ሁልጊዜ ከቤተሰባችን አባላት ሁሉ ከእንቅልፍ ለመነሳት የመጀመሪያዋና ወደ መኝታ ለመሄድ የመጨረሻዋ ነበረች፤ ቤቱን እንደሚጠበቀው ለማሠጋደድ፣ ልብሶቻችንን ለማስተካከል፣ መጻህፍታችንንና በትምህርት ቤት የሚጠበቁብንን ጉዳዮች ለማዘገጃጀትና የአባቴን የሥራ ወረቀቶች ለማደራጀት ከሁላችንም በፊት ቀድማ እየተነሣች ትለፋለች፡፡ ልብሶቻችንን ሁሉ እሷው በልካችን ትሰፋለች፣ ጸጉራችንን ትቆርጣለች፤ ቤቱንም በእጅ ሥራዎች ጌጦች ታሸበርቀዋለች፡፡ ለቁርሳችን የምትሠራው ፎሶሊያ የሚለማው እኛ ጠዋት ከመኝታችን ሳንነሳ እማማ በምትንከባከበው በጓሮ አትክልት ማሳችን ነው፡፡ እህሉን ቃኝታ ለቀን ሠራተኞቹ የእርሻ መሣሪያዎች ታከፋፍልና ላሞቻችንና ሌሎቹ እንስሶቻችን እንዲቀለቡና እንዲታጠቡ ታደርጋለች፡፡ እነዚህን የማለዳ ሥራዎቿን ከጨራረሰች በኋላ እኛን ወደ ትምህርት ቤት ትሸኝና በእግሯ ቁልቁል መንገዱን ይዛ የሙሉ ጊዜ የማስተማር ሥራዋን ለመጀመር በአቅራቢያችን ወዳለው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ትሄዳለች፡፡
ወላጆቼ መምህራን ነበሩ፡፡ ድህነትንና ርሃብን ብቸኛው መመከቻም ትምህርት እንደሆነ በጽኑ ያምናሉ፡፡ በቆዳ ስፋቷ ከሞላ ጎደል ጂቡቲን የምታክለው ሩዋንዳ ከአፍሪካ ትናንሽ ሀገራት አንዷ ብትሆንም በአህጉሩ በከፍተኛ የሕዝብ ጥግግት ተጠቃሽና ከዓለምም ደሃ ሀገራት አንዷ ነች፡፡ እናቴና አባቴ ከየቤተሰቦቻቸው የመጀመሪያዎቹ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቁ ሰዎች ሲሆኑ ልጆቻቸው እነርሱ ከደረሱበትም በላይ እንድንደርስላቸው ቆርጠዋል፡፡ አባባ ጠንክሮ በመሥራትና በሕይወቱ ሙሉ በማጥናት አርዓያ ሆኖናል፡፡ በሥራ ሕይወቱ ብዙ ክብሮችንና ዕድገቶችን ያገኘ ሲሆን፤ በአጭር ጊዜም ከአንደኛ ደረጃ መምህርነት ወደ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርነት አድጓል፡፡ በኋላም በአውራጃችን ላሉት ለሁሉም የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች ዋና አስተዳዳሪ ሆኖ ተሾሟል፡፡ በሩዋንዳ እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ልዩ የሆነ መጠሪያ ስም አለው፡፡ ለእያንዳንዱ ልጅ ወላጆች ልጁ ሲወለድ እናቱ ወይንም አባቱ መጀመሪያ ባዩት ጊዜ የተሰማቸውን ስሜት የሚያንጸባርቅ ስም ይሰጡታል፡፡ ኪንያሩዋንዳ በሚባለው ያገራችን ቋንቋ የኔ ስም (ኢሊባጊዛ) ትርጉሙ ‹‹መንፈሰ-ብሩህና ግሩም ጸዳል ያላት›› ማለት ነው፡፡ ይህን ስም ያወጣልኝ አባቴ ከተወለድኩባት ቅጽበት ጀምሮ ምን ያህል እንደሚወደኝ ስሜ ሁልጊዜ ሲያስታውሰኝ ይኖራል፡፡
የአባቴ ስም ሊኦናርድ፣ የእናቴ ደግሞ ማሬ ሮዝ ሲሆን፤ እናቴን ባልንጀሮቿ ሮዝ እያሉ ይጠሯታል፡፡ በ1963 ክረምት በአንደኛዋ የአክስቴ ልጅ ቤት ወላጆቼ ወደጋራ ጓደኛቸው ሰርግ ሲሄዱ ይገናኛሉ፡፡ ሲተዋወቁ አባቴ ጸጉሩ አድጎ እንደነገሩ ስለነበር እናቴ አየት አድርጋው ከንፈሯን መጠጠችለት፡፡
‹‹ጸጉርህ እንደዚህ ሆኖ ሰርግ ልትሄድ ነው?›› በማለት በቁጭት ጠየቀችው፡፡ አባቴ ጸጉር አስተካካይ ማግኘት እንዳልቻለ ገልጾ ‹ምን ላድርገው ብለሽ ነው› በሚል ስሜት ትከሻውን ነቀነቀ፡፡ ወዲያውኑ እዚያው እናቴ መቀስ ፈልጋ አባቴን አመቺ ስፍራ አስቀመጠችና ጸጉሩን ማስተካከል ጀመረች፡፡ ጸጉር ቆረጣውን እንዳሳመረችው አይጠረጠርም - ከዚያ ጀምሮ አልተለያዩምና፡፡ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ታጋብተው አባቴ ከዚያ በኋላ እናቴ እንጂ ሌላ ማንም ሰው ጸጉሩን እንደማያስተካክለው አረጋገጠ፡፡
ወላጆቼ በማስተማር ሥራቸውና አያቴ የሰጣቸውን መሬት በማረስ (ባቄላ፣ ሙዝና ቡና እያመረቱ ይሸጡ ነበር) ከሚያገኙት ገቢ ትንሽ ገንዘብ መቆጠብ ቻሉ
❤3👍3
#ሁቱትሲ
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ምዕራፍ_ሁለት
#ከመቀመጫችን_ሲያስነሡን
‹‹ቱትሲዎች ከመቀመጫችሁ ተነሡ!››
አንድ ቀን አራተኛ ክፍል ሆኜ እማርበት በነበረው መማሪያ ክፍል ውስጥ ስድስት ልጆች ከመቀመጫቸው ተስፈንጥረው ሲቆሙ ግማሽ ደርዘን ወንበሮች ወደ ኋላ ተንጓጉ፡፡ ከዚያ በፊት ሁልጊዜ እናቴ በምታስተምርበት አነስተኛ ትምህርት ቤት ውስጥ እማር ስለነበር ምን እየተከሰተ እንደነበር ልገምት አልቻልኩም፡፡ በዚያን ወቅት አሥር አመቴ ስለነበርና ትንሽ አደግ ላሉ ልጆች የሚሆን ትምህርት ቤት ውስጥ ስማር የመጀመሪያ ቀኔ በመሆኑ የልጆቹ መራበሽ ግራ አጋብቶኛል፡፡ ከዚያ በፊት አስተማሪ የዘውግ ጥሪ ሲያካሂድ በፍጹም አይቼ አላውቅም፡፡
‹‹ቱትሲዎች በሙሉ ከመቀመጫችሁ ተነሡ!›› መምህራችን፣ ቡሆሮ፣ አምባረቀ፡፡ በትልቅ እርሳስ ከዝርዝሩ ላይ ከተማሪዎች ስም አጠገብ ምልክት እያደረገ ነበር፡፡ ከዚያም አቆመና በቀጥታ እኔ ላይ አፈጠጠ፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ፣ ሁቱ ስል አልተነሣሽም፤ ትዋ ስል አልተነሣሽም፤ አሁንም ቱትሲ ብል ልትነሺ አልቻልሽም፡፡ ለምንድነው?›› ቦሆሮ ፈገግ እያለ ቢሆንም ድምጹ ግን ክፋቱን ያሳብቅበታል፡፡
‹‹አላውቅም መምህር፡፡››
‹‹ምን ዘውግ ነሽ?››
‹‹የት አውቃለሁ፣ መምህር?››
‹‹ሁቱ ነሽ ቱትሲ?››
‹‹እኔ - እኔ አላውቅም፡፡››
‹‹ካላወቅሽ ውጪያ! ከዚህ ክፍል ውጪ፤ እና ምን እንደሆንሽ ሳታውቂ ተመልሰሽ አትምጪ!››
መጻሕፍቴን ሰበሰብኩና በሃፍረት አንገቴን ደፍቼ ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ ገና ያልታወቀኝ ቢሆንም በሩዋንዳ የዘውግ ክፍፍል ላይ የመጀመሪያዋን ትምህርቴን
ተማርኩ፤ ይህም ክው ነበር ያደረገኝ፡፡
ወደ ትምህርት ቤቱ ጓሮ ሮጬ ወንድሜ ዳማሲን የዕለቱን ትምህርት እስኪጨርስ ድረስ ከቁጥቋጦ ጀርባ ተደብቄ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ እንባዬን ማቆም ተስኖኝ ሰማያዊ የትምህርት ቤት የደንብ ልብሴ እስኪረጥብ ድረስ ነፈረቅሁ፡፡ ምን እንደተከሰተ ስላልገባኝ ወደ ክፍል ሄጄ የቅርብ ጓደኛዬን ዣኔትን ጉዳዩን ታብራራልኝ ዘንድ ለመጠየቅ በጣም ፈለግሁ፡፡ መምህሩ ሁቱ የሚለውን ስም ሲጠራ ተነሥታለች - ምን አልባትም መምህሩ ለምን እንዳመናጨቀኝ ታውቅ ይሆናል፡፡ በቁጥቋጦው ውስጥ ተኮራምቼ ዳማሲን እዚያ እስኪያገኘኝ ድረስ እንባዬን ሳዘራ ቆየሁ፡፡
‹‹ማን መታሽ ኢማኪዩሌ?›› ሲል ታላቅ ወንድሜ ባለችው የ13 ዓመት ሥልጣን ጠየቀኝ፡፡ አለኝታዬ ዳማሲን አንድ ሰው ጫፌን ከነካኝ ለመፋለም የተዘጋጀ ልጅ ነው፡፡ ቡሆሮ ያለኝን ነገርኩት፡፡
‹‹ቡሆሮ ጥሩ ሰው አይደለም›› አለ ወንድሜ፡፡ ‹‹ቢሆንም አትጨነቂለት፡፡ ሌላ ቀን ስም ሲጠራ እኔ የማደርገውን አድርጊ፤ ከጓደኞችሽ ጋር ተነሺ፡፡ ጓደኛሽ ዣኔት ስትነሳ ተነሺ፡፡››
‹‹ዣኔት ሁቱ ብሎ ሲጠራ ነበር የተነሣችው፡፡››
‹‹በቃ እንደዚያ ከሆነ ሁቱ ሲሉ ተነሺ፡፡ ጓደኞቻችን የሆኑት ያንን ከሆነ መቼም እኛም የምንሆነው እንደዚያው መሆን አለበት፡፡ ሁላችንም አንድ ሕዝብ ነን፣ አይደል?››
በዚያን ወቅት የማውቅበት መንገድ አልነበረኝም፤ ዳማሲንም እንደኔው በሩዋንዳ ስለነበረው ዘውገኝነት ግንዛቤ አልነበረውም… ይህም በአካባቢው በጥሩ ሁኔታ ይማሩ ከነበሩት ልጆች ውስጥ ከመመደባችን አንጻር እንግዳ ነገር ነው፡፡ በየዕለቱ ከትምህርት መልስ ወንድሞቼና እኔ ወደ ቤታችን በእናታችን ተቆጣጣሪነት የቤት ሥራችንን እንድንሠራ ከመጠራታችን በፊት የ90 ደቂቃ የእረፍት ጊዜ ነበረን፡፡ አባታችን ከራት በፊት የትምህርት ቤታችንን ሰሌዳዎች የምታክል ጥቁር ሰሌዳ በቤታችን መካከል አድርጎ ከአንድ ሰዓት ለሚበልጥ ጊዜ ያስጠናናል፡፡ የሒሳብ፣ ሰዋስውና መልክዓምድር ጥናት ጠመኔ እየሰጠ ያለማምደናል፡፡
ይሁን እንጂ ወላጆቻችን ስለራሳችን ታሪክ አላስተማሩንም፡፡ ሩዋንዳ የሦስት ዘውጎች፣ ማለትም የሚበዛው ሁቱ፣ አናሳ ቱትሲዎችና በጣም ትንሽ ቁጥር ያላቸው በጫካ ውስጥ የሚኖሩት ትዋዎች ስብስብ እንደሆነች አላስገነዘቡንም፡፡ የጀርመን ቅኝ ገዥዎችና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ቤልጅየሞች የሩዋንዳን ነባር ማኅበራዊ አወቃቀር ማለትም ሩዋንዳን ለምዕተ-ዓመታት ሰላምና ስምምነት የሰጣት ቱትሲ ንጉሥ የሚመሩትን ዘውዳዊውን ሥርዓት በአግላይ ዘውግ-ተኮር የመደብ ሥርዓት ቀይረውት እንደነበር አልተማርንም፡፡ ቤልጅየማውያኑ የቱትሲውን ገዥ መደብ ደግፈውና በመሪነት ደረጃ ያለውን አስተዋፅኦም ተቀብለው፣ አገሪቱን በተሻለ መንገድ ለማስተዳደርና ለቤልጅየማውያኑ ከፍተኛ ትርፍ ለማስገኘት ያግዝ ዘንድ ቱትሲዎች የተሻለ ትምህርት እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡ ቤልጅየሞች በሁቱና ቱትሲ መካከል ፈጥረውት የነበረውን ክፍተት በማባባስ ሁለቱን ዘውጎች በቀላሉ ለመለየት የዘውግ መታወቂያ ደብተር አስተዋውቀዋል፡፡ እነዚያ የማይረቡ ስህተቶችም በሁቱዎች ዘንድ ዘላቂ ቁጭት በመፍጠር ለዘር ጭፍጨፋ መሠረት ለመጣል አገዙ፡፡ ቱትሲዎች የተሻለ ነጻነት በጠየቁ ጊዜ ቤልጅየማውያኑ በጠላትነት አዩአቸው፡፡ በ1959 ደም-አፋሳሽ የሁቱ አመፅን ደግፈው ዘውዳዊው ሥርዓት እንዲገረሰስ አደረጉ፡፡ ከ100 000 በላይ ቱትሲዎች በበቀል በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት ውስጥ ተገደሉ፡፡ በ1962 ቤልጅዬም ከሩዋንዳ ለቃ ስትወጣ የሁቱ መንግሥት አንቀጥቅጦ በመግዛት ላይ ሲሆን ቱትሲዎችም በሁቱ አክራሪዎች ማሳደድ፣ ሽብርና ግድያ የሚፈጸምባቸው ሁለተኛ ዜጎች ለመሆን በቁ፡፡ በብዙ አሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች ግድያዎች የዕለት ከዕለት ክስተት በነበሩባቸው አሥርት ዓመታት ውስጥ ሞቱ፡፡ የሽብር ዑደቱ ተጧጡፎ መድሎ መፈጸሙ ቀጠለ፡፡ የሁቱው መንግሥት ከቤልጅየሞች የአገዛዝ ዘመናት የወሰደው የዘውግ መታወቂያ ደብተር አሠራር መድሎውን የበለጠ ይፋና ቀላል አደረገው፡፡
ወላጆቻችን እኔና ወንድሞቼ ቢያንስ በልጅነታችን እንዳንማራቸው ያልፈለጓቸው የታሪክ ትምህርቶች እነዚህ ነበሩ፡፡ ስለ መድሎም ሆነ ስለ ግድያ ዘመቻዎቹ፣ ስለ ዘር ማጽዳቱም ሆነ የዘር መታወቂያ ካርዶቹ አላወሩንም - እነዚህ ነገሮች ፈጽሞ የልጅነቴ አካል አልነበሩም፡፡
ዘርን፣ ሃይማኖትን ወይንም ዘውግን ከግምት ውስጥ ሳናስገባ በቤታችን ማንንም ሰው በደስታ እንቀበላለን፡፡ ወላጆቼ የእርስዎን ሁቱ ወይንም ቱትሲ መሆን ከስብዕናዎ ጋር አያገናኙትም፡፡ ጥሩ ጸባይ ካለዎትና ገራገር ከሆኑ እጆቻቸውን ዘርግተው ሰላምታ ያቀርቡልዎታል፡፡ ወላጆቼ ራሳቸው ግን በሁቱ ጽንፈኞች የደረሱባቸው የተወሰኑ አሰቃቂ ችግሮች ነበሩ … እንዲያውም አንደኛውን ትንሽ ትንሽ አስታውሳለሁ፡፡ ያኔ የሦስት ዓመት ልጅ ነኝ፡፡ ነፍስ ባለማወቄ ምን እየተከሰተ እንደነበር አልገባኝም፡፡ የምሽቱን ሰማይ እሳት ሲንቦገቦግበት፣ እናቴም በእጆቿ ጥብቅ አድርጋ ታቅፋኝ ከቤታችን ስትሮጥ ይታወሰኛል፡፡ ይህ የሆነው ብዙ ቱትሲዎች በተሳደዱበት፣ ከቤቶቻቸው በተነዱበትና በየመንገዱ በተገደሉበት የ1973ቱ መፈንቅለ-መንግሥት ወቅት መሆኑ ነው፡፡ በኛ ክፍለሀገር ሁቱ ጽንፈኞች የቱትሲዎችን ቤቶች በየተራ አቃጥለዋል፡፡ እሳቱ ወደኛ ሽቅብ ሲገሰግስ መላው ቤተሰቤ አብሮ ቆሞ ወደ ኪቩ ሐይቅ ቁልቁል በማስተዋል ላይ ነበረ፡፡ ሩታካሚዜ ወደተባለው ጥሩ ሁቱ ወዳጅ ጎረቤታችን ቤት ሸሸን፡፡ እርሱም ግድያዎቹና ቃጠሎው እስኪያቆሙ ድረስ ሸሸገን፡፡ ወደ ቤታችን ስንመለስ የሚጫጫስ
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ምዕራፍ_ሁለት
#ከመቀመጫችን_ሲያስነሡን
‹‹ቱትሲዎች ከመቀመጫችሁ ተነሡ!››
አንድ ቀን አራተኛ ክፍል ሆኜ እማርበት በነበረው መማሪያ ክፍል ውስጥ ስድስት ልጆች ከመቀመጫቸው ተስፈንጥረው ሲቆሙ ግማሽ ደርዘን ወንበሮች ወደ ኋላ ተንጓጉ፡፡ ከዚያ በፊት ሁልጊዜ እናቴ በምታስተምርበት አነስተኛ ትምህርት ቤት ውስጥ እማር ስለነበር ምን እየተከሰተ እንደነበር ልገምት አልቻልኩም፡፡ በዚያን ወቅት አሥር አመቴ ስለነበርና ትንሽ አደግ ላሉ ልጆች የሚሆን ትምህርት ቤት ውስጥ ስማር የመጀመሪያ ቀኔ በመሆኑ የልጆቹ መራበሽ ግራ አጋብቶኛል፡፡ ከዚያ በፊት አስተማሪ የዘውግ ጥሪ ሲያካሂድ በፍጹም አይቼ አላውቅም፡፡
‹‹ቱትሲዎች በሙሉ ከመቀመጫችሁ ተነሡ!›› መምህራችን፣ ቡሆሮ፣ አምባረቀ፡፡ በትልቅ እርሳስ ከዝርዝሩ ላይ ከተማሪዎች ስም አጠገብ ምልክት እያደረገ ነበር፡፡ ከዚያም አቆመና በቀጥታ እኔ ላይ አፈጠጠ፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ፣ ሁቱ ስል አልተነሣሽም፤ ትዋ ስል አልተነሣሽም፤ አሁንም ቱትሲ ብል ልትነሺ አልቻልሽም፡፡ ለምንድነው?›› ቦሆሮ ፈገግ እያለ ቢሆንም ድምጹ ግን ክፋቱን ያሳብቅበታል፡፡
‹‹አላውቅም መምህር፡፡››
‹‹ምን ዘውግ ነሽ?››
‹‹የት አውቃለሁ፣ መምህር?››
‹‹ሁቱ ነሽ ቱትሲ?››
‹‹እኔ - እኔ አላውቅም፡፡››
‹‹ካላወቅሽ ውጪያ! ከዚህ ክፍል ውጪ፤ እና ምን እንደሆንሽ ሳታውቂ ተመልሰሽ አትምጪ!››
መጻሕፍቴን ሰበሰብኩና በሃፍረት አንገቴን ደፍቼ ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ ገና ያልታወቀኝ ቢሆንም በሩዋንዳ የዘውግ ክፍፍል ላይ የመጀመሪያዋን ትምህርቴን
ተማርኩ፤ ይህም ክው ነበር ያደረገኝ፡፡
ወደ ትምህርት ቤቱ ጓሮ ሮጬ ወንድሜ ዳማሲን የዕለቱን ትምህርት እስኪጨርስ ድረስ ከቁጥቋጦ ጀርባ ተደብቄ መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ እንባዬን ማቆም ተስኖኝ ሰማያዊ የትምህርት ቤት የደንብ ልብሴ እስኪረጥብ ድረስ ነፈረቅሁ፡፡ ምን እንደተከሰተ ስላልገባኝ ወደ ክፍል ሄጄ የቅርብ ጓደኛዬን ዣኔትን ጉዳዩን ታብራራልኝ ዘንድ ለመጠየቅ በጣም ፈለግሁ፡፡ መምህሩ ሁቱ የሚለውን ስም ሲጠራ ተነሥታለች - ምን አልባትም መምህሩ ለምን እንዳመናጨቀኝ ታውቅ ይሆናል፡፡ በቁጥቋጦው ውስጥ ተኮራምቼ ዳማሲን እዚያ እስኪያገኘኝ ድረስ እንባዬን ሳዘራ ቆየሁ፡፡
‹‹ማን መታሽ ኢማኪዩሌ?›› ሲል ታላቅ ወንድሜ ባለችው የ13 ዓመት ሥልጣን ጠየቀኝ፡፡ አለኝታዬ ዳማሲን አንድ ሰው ጫፌን ከነካኝ ለመፋለም የተዘጋጀ ልጅ ነው፡፡ ቡሆሮ ያለኝን ነገርኩት፡፡
‹‹ቡሆሮ ጥሩ ሰው አይደለም›› አለ ወንድሜ፡፡ ‹‹ቢሆንም አትጨነቂለት፡፡ ሌላ ቀን ስም ሲጠራ እኔ የማደርገውን አድርጊ፤ ከጓደኞችሽ ጋር ተነሺ፡፡ ጓደኛሽ ዣኔት ስትነሳ ተነሺ፡፡››
‹‹ዣኔት ሁቱ ብሎ ሲጠራ ነበር የተነሣችው፡፡››
‹‹በቃ እንደዚያ ከሆነ ሁቱ ሲሉ ተነሺ፡፡ ጓደኞቻችን የሆኑት ያንን ከሆነ መቼም እኛም የምንሆነው እንደዚያው መሆን አለበት፡፡ ሁላችንም አንድ ሕዝብ ነን፣ አይደል?››
በዚያን ወቅት የማውቅበት መንገድ አልነበረኝም፤ ዳማሲንም እንደኔው በሩዋንዳ ስለነበረው ዘውገኝነት ግንዛቤ አልነበረውም… ይህም በአካባቢው በጥሩ ሁኔታ ይማሩ ከነበሩት ልጆች ውስጥ ከመመደባችን አንጻር እንግዳ ነገር ነው፡፡ በየዕለቱ ከትምህርት መልስ ወንድሞቼና እኔ ወደ ቤታችን በእናታችን ተቆጣጣሪነት የቤት ሥራችንን እንድንሠራ ከመጠራታችን በፊት የ90 ደቂቃ የእረፍት ጊዜ ነበረን፡፡ አባታችን ከራት በፊት የትምህርት ቤታችንን ሰሌዳዎች የምታክል ጥቁር ሰሌዳ በቤታችን መካከል አድርጎ ከአንድ ሰዓት ለሚበልጥ ጊዜ ያስጠናናል፡፡ የሒሳብ፣ ሰዋስውና መልክዓምድር ጥናት ጠመኔ እየሰጠ ያለማምደናል፡፡
ይሁን እንጂ ወላጆቻችን ስለራሳችን ታሪክ አላስተማሩንም፡፡ ሩዋንዳ የሦስት ዘውጎች፣ ማለትም የሚበዛው ሁቱ፣ አናሳ ቱትሲዎችና በጣም ትንሽ ቁጥር ያላቸው በጫካ ውስጥ የሚኖሩት ትዋዎች ስብስብ እንደሆነች አላስገነዘቡንም፡፡ የጀርመን ቅኝ ገዥዎችና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ቤልጅየሞች የሩዋንዳን ነባር ማኅበራዊ አወቃቀር ማለትም ሩዋንዳን ለምዕተ-ዓመታት ሰላምና ስምምነት የሰጣት ቱትሲ ንጉሥ የሚመሩትን ዘውዳዊውን ሥርዓት በአግላይ ዘውግ-ተኮር የመደብ ሥርዓት ቀይረውት እንደነበር አልተማርንም፡፡ ቤልጅየማውያኑ የቱትሲውን ገዥ መደብ ደግፈውና በመሪነት ደረጃ ያለውን አስተዋፅኦም ተቀብለው፣ አገሪቱን በተሻለ መንገድ ለማስተዳደርና ለቤልጅየማውያኑ ከፍተኛ ትርፍ ለማስገኘት ያግዝ ዘንድ ቱትሲዎች የተሻለ ትምህርት እንዲያገኙ አድርገዋል፡፡ ቤልጅየሞች በሁቱና ቱትሲ መካከል ፈጥረውት የነበረውን ክፍተት በማባባስ ሁለቱን ዘውጎች በቀላሉ ለመለየት የዘውግ መታወቂያ ደብተር አስተዋውቀዋል፡፡ እነዚያ የማይረቡ ስህተቶችም በሁቱዎች ዘንድ ዘላቂ ቁጭት በመፍጠር ለዘር ጭፍጨፋ መሠረት ለመጣል አገዙ፡፡ ቱትሲዎች የተሻለ ነጻነት በጠየቁ ጊዜ ቤልጅየማውያኑ በጠላትነት አዩአቸው፡፡ በ1959 ደም-አፋሳሽ የሁቱ አመፅን ደግፈው ዘውዳዊው ሥርዓት እንዲገረሰስ አደረጉ፡፡ ከ100 000 በላይ ቱትሲዎች በበቀል በቀጣዮቹ ጥቂት ዓመታት ውስጥ ተገደሉ፡፡ በ1962 ቤልጅዬም ከሩዋንዳ ለቃ ስትወጣ የሁቱ መንግሥት አንቀጥቅጦ በመግዛት ላይ ሲሆን ቱትሲዎችም በሁቱ አክራሪዎች ማሳደድ፣ ሽብርና ግድያ የሚፈጸምባቸው ሁለተኛ ዜጎች ለመሆን በቁ፡፡ በብዙ አሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች ግድያዎች የዕለት ከዕለት ክስተት በነበሩባቸው አሥርት ዓመታት ውስጥ ሞቱ፡፡ የሽብር ዑደቱ ተጧጡፎ መድሎ መፈጸሙ ቀጠለ፡፡ የሁቱው መንግሥት ከቤልጅየሞች የአገዛዝ ዘመናት የወሰደው የዘውግ መታወቂያ ደብተር አሠራር መድሎውን የበለጠ ይፋና ቀላል አደረገው፡፡
ወላጆቻችን እኔና ወንድሞቼ ቢያንስ በልጅነታችን እንዳንማራቸው ያልፈለጓቸው የታሪክ ትምህርቶች እነዚህ ነበሩ፡፡ ስለ መድሎም ሆነ ስለ ግድያ ዘመቻዎቹ፣ ስለ ዘር ማጽዳቱም ሆነ የዘር መታወቂያ ካርዶቹ አላወሩንም - እነዚህ ነገሮች ፈጽሞ የልጅነቴ አካል አልነበሩም፡፡
ዘርን፣ ሃይማኖትን ወይንም ዘውግን ከግምት ውስጥ ሳናስገባ በቤታችን ማንንም ሰው በደስታ እንቀበላለን፡፡ ወላጆቼ የእርስዎን ሁቱ ወይንም ቱትሲ መሆን ከስብዕናዎ ጋር አያገናኙትም፡፡ ጥሩ ጸባይ ካለዎትና ገራገር ከሆኑ እጆቻቸውን ዘርግተው ሰላምታ ያቀርቡልዎታል፡፡ ወላጆቼ ራሳቸው ግን በሁቱ ጽንፈኞች የደረሱባቸው የተወሰኑ አሰቃቂ ችግሮች ነበሩ … እንዲያውም አንደኛውን ትንሽ ትንሽ አስታውሳለሁ፡፡ ያኔ የሦስት ዓመት ልጅ ነኝ፡፡ ነፍስ ባለማወቄ ምን እየተከሰተ እንደነበር አልገባኝም፡፡ የምሽቱን ሰማይ እሳት ሲንቦገቦግበት፣ እናቴም በእጆቿ ጥብቅ አድርጋ ታቅፋኝ ከቤታችን ስትሮጥ ይታወሰኛል፡፡ ይህ የሆነው ብዙ ቱትሲዎች በተሳደዱበት፣ ከቤቶቻቸው በተነዱበትና በየመንገዱ በተገደሉበት የ1973ቱ መፈንቅለ-መንግሥት ወቅት መሆኑ ነው፡፡ በኛ ክፍለሀገር ሁቱ ጽንፈኞች የቱትሲዎችን ቤቶች በየተራ አቃጥለዋል፡፡ እሳቱ ወደኛ ሽቅብ ሲገሰግስ መላው ቤተሰቤ አብሮ ቆሞ ወደ ኪቩ ሐይቅ ቁልቁል በማስተዋል ላይ ነበረ፡፡ ሩታካሚዜ ወደተባለው ጥሩ ሁቱ ወዳጅ ጎረቤታችን ቤት ሸሸን፡፡ እርሱም ግድያዎቹና ቃጠሎው እስኪያቆሙ ድረስ ሸሸገን፡፡ ወደ ቤታችን ስንመለስ የሚጫጫስ
👍2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_ሦስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ቅድመ_ከፍተኛ_ትምህርት
በሦስተኛውና በመጨረሻው ዓመት ጦርነት ከመፈንዳቱ በቀር ሕይወት በሊሴ ጥሩ ነበር፡፡
የ1990 የጥቅምት ወር የመጀመሪያዋ ቀን ከሰዓት ቆንጆና ብሩህ ነበረች፡፡ የክፍል ጓደኞቼና እኔ የግብረገብ ትምህርት ክፍለጊዜያችን እስኪጀምር እየጠበቅን መምህሩ ለምን እንደዘገየ እናስባለን፡፡ አቶ ጋሂጊ ለመግባባት የማያስቸግር፣ የተረጋጋና ምናልባትም ካገኘኋቸው ሰዎች ሁሉ ልስልስ ጸባይ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም በመጨረሻ እጆቹን አያይዞ ሲመጣና በክፍሉ ፊትለፊት ወደፊትና ወደኋላ ሄድ መለስ ሲል አንዳች ነገር እንደተከሰተ ገምተናል፡፡ አንደኛዋ ተማሪ ችግሩ ምን እንደሆነ ብትጠይቀውም ወደ እኛ ሳያይ መለስ ቀለስ ማለቱን ቀጠለ፡፡
መምህራችን አንዳች መጥፎ ዜና እንደደበቀንና ምን አልባትም የተንቀሳቃሽ ምስል ትዕይንት ምሽትን መነኩሲቶቹ ሰርዘውት እንደሆነ ሊነግረን ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ጉዳዩ ግን ከዚያ የባሰ ነበር፡፡ በትምህርት ቤት ውስጥ የዜና ዘገባዎችን ማዳመጥ ስለማይፈቀድልን በመኖሪያ ቤቴ እንደነበረው ሁሉ ከዓለም ወሬ ተነጥያለሁ፡፡
‹‹በሀገሪቱ ላይ ጥቃት እንደተፈጸመ ሰማሁ›› ሲል አቶ ጋሂጊ በሃዘኔታ ነገረን፡፡ ‹‹በጣም አደገኛና በሁላችንም ላይ ለረጅም ጊዜ ተጽዕኖ የሚኖረው ይሆናል ብዬ እፈራለሁ፡፡››
ክፍሉ በጸጥታ ተዋጠ - ከዚያ ሁሉም ባንዴ ማውራት ጀመረ፣ ጥያቄ መጠያየቅ፣ ሩዋንዳን ማን ለምን እንደሚያጠቃት ለማወቅ መጠባበቅ፡፡
‹‹በዩጋንዳ የሚኖር የአማጽያን ቡድን የአገሪቱን ድንበር አቋርጧል›› ሲል መለሰልን፡፡ ‹‹በዋነኝነት ከሩዋንዳ የሄዱ ጥገኞች ልጆች ሲሆኑ ተሰባስበው ወደ ሀገሪቱ ለመግባት እየተዋጉ ነው፡፡ ከዚህ ስፍራ በስተሰሜን በኩል በአሁኑ ሰዓት በአማጽያንና በሩዋንዳ መንግሥት ወታደሮች መካከል ከባድ ውጊያ በመካሄድ ላይ ነው፡፡›› አቶ ጋሂጊ ፍርሃትና ንዴትን የሚያንጸባርቅ የጥያቄዎች ዝናብ ወረደበት፡፡ ‹‹ቱትሲዎቹ ሽፍቶች ግን ምንድን ነው የሚፈልጉት? ለምን ጦርነት ይከፍቱብናል? ትምህርት ቤቱ ጋር ከደረሱስ ምን ያደርጉን ይሆን?››
የሃፍረት ሙቀት በማጅራቴ ተሰማኝ፤ በማስደገፊያዬም ስር ለመደበቅ ፈለግሁ፡፡ በክፍሉ ውስጥ ካለነው 50 ተማሪዎች 47ቱ ሁቱዎች ናቸው፡፡ በጣም ስለፈራሁና ስለራሴ ስለተጨነቅሁ ሌሎቹን ሁለት ቱትሲ ልጃገረዶች ማየት እንኳን ተሳነኝ፡፡ በቱትሲነቴ ሳፍርና በሊሴም ተለይቼ ስታይ የመጀመሪያዬ ነው፡፡
‹‹አማጽያኑ ራሳቸውን የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር (ሩአግ) ብለው አደራጅተዋል፡፡ ቡድኑ ሩዋንዳን ከዓመታት በፊት ለቀው የሄዱና እንዳይመለሱ የተከለከሉ የቱትሲዎች ድርጅት ነው፡፡ እነዚህ የውጪ ዜጎች ወደ ሩዋንዳ በመግባት መንግሥታዊውን ለመያዝ ጦርነት አውጀውብናል›› አለ፡፡
ስለ ሩአግ ምንነት ግንዛቤው ነበረኝ፡፡ አባላቱ መንግሥትን ለመጣል ሲሉ ብቻ እንደማይዋጉም አውቃለሁ፡፡ እኩልነት በሰፈነባትና በነጻ ሀገር መኖርን ይፈልጋሉ፡፡ አብዛኞቹ የሩአግ ወታደሮች ስደተኞች ቱትሲዎች ወይንም ልጆቻቸው ናቸው፡፡
በ1959ና በ1973ቱ ችግሮች እንዲሁም ሁቱ ጽንፈኞች የግድያ ዘመቻዎችን ባካሄዱባቸው ሌሎች በርካታ ጊዜያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሕይወት ለማዳን ከሩዋንዳ ሸሽተዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ አማጽያኑን ‹‹የውጪ ዜጎች›› ያላቸው አብዛኞቹ እንደ ዩጋንዳና ዛየር ባሉ ጎረቤት ሀገራት ስላደጉ ነው - ያ የሆነው ግን ርዕሰ-ብሔር ሃብያሪማና ስደተኞች ፈጽሞ ወደ ሀገራቸው አንዳይመለሱ የሚከለክል ሕግ ስላወጡ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ግዙፍ የቱትሲ ስደተኞች ስብስብ እንዲፈጠር ያደረጉ ሲሆን አንድ ሙሉ የሩዋንዳ ቱትሲዎች ትውልድንም አንዴ እንኳን የእናት አገሩን አፈር ሳይረግጥ እንዲያድግ አስገድደዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ ያንን ፈጽሞ ባይገልጽም ቱትሲዎች ራሳቸውን ከጽንፈኛ ሁቱዎች ለመከላከል በሞከሩ ቁጥር ግን ምን እንደሚከሰት ያውቃል፡፡ ለእኛ መጨነቁን ‹‹ይህ ለቱትሲዎች በጣም አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል - ይህን ዓይነት ነገር ወደ ብዙ ግድያዎች ሊያመራ ስለሚችል መንግሥትና አማጽያኑ ችግራቸውን እንዲፈቱና ደም መፋሰስ እንዲቆም እንጸልይ፡፡››
የዕለቱ ትምህርታችን በዚሁ አበቃ፡፡ ሴቶቹ ልጆች ግን የሚያወሩት ስለጥቃቱና ቱትሲ ወታደሮቹ ወደ ትምህርት ቤታችን ቢደርሱ ምን ማድረግ እንደሚኖርባቸው ብቻ ሆነ፡፡ ከሁለት ቱትሲ የክፍል ጓደኞቼ ጋር ጸጥ ብዬ ላለመታየት እየሞከርኩ ተቀመጥሁ፡፡ ቱትሲዎች እንዴት ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደተያዙ ሳስብ ሃፍረቴ ወደ ንዴት ተለወጠ፡፡ የመንግሥት ወታደሮችን አሸንፎ ለመድሎው ፍጻሜ ያበጅለት ዘንድ ተስፋ በማድረግ በልቤ ለሩአግ አጋርነቴን አሳየሁ፡፡ በመጨረሻ ግን ንዴቴ ወደ ፍራቻ የተቀየረው ስለመንደሬና ስለቤተሰቤ በተጨነቅሁ ጊዜ ነው፡፡ አምላኬ ቤተሰቤን ሰላም ያደርግልኝ ዘንድ ዓይኖቼን ጨፍኜ ተማጸንኩት - በወቅቱ ያለ-ነሱ እንዴት በሕይወት እንደምቆይ ስለማላውቅ፡፡
ብዙዎቹ ተማሪዎች ጦርነቱ አስከፊ በነበረበት በሰሜኑ ክፍል ዘመዶች ስለነበሯቸው የትምህርት ቤቱ ርዕሰ - መምህር የሬድዮ ዘገባ እንድናዳምጥና ስለ ክስተቱ እንድንረዳ ፈቀደልን፡፡ ብሄራዊው ሬድዮ የሚያስተላልፈው ዘገባ ከሞላ ጎደል የጥላቻ ውትወታ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዘጋቢዎቹ አማጽያኑ እንደ አውሬ በጫካ እንደሚኖሩ፣ የሰው ስጋ እንደሚበሉና ከዝንጀሮዎች ጋር ወሲብ እንደሚፈጽሙ አተቱ፡፡ የለየላቸው ሰይጣኖች ስለሆኑ ቀንድ አብቅለዋል ተባለ፡፡ ‹‹አማጽያን በረሮዎቹ›› በማናቸውም ስፍራና ጊዜ ሊተናኮሉ ስለሚችሉና መሰሪ ስለሆኑ ሩዋንዳውያን ራሳቸውን እንዲጠብቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው፡፡ እነዚህ ዘገባዎች ቀድሞውንም የተዛባ አመለካከት የነበራቸውን ልጃገረዶች አቀጣጠሏቸው፡፡ አንዷማ በጣም ፈርታ ስለነበር ልታስገድለኝ ነበር፡፡
ዳኒዳ ከመኝታ ቤት እህቶቼ አንዷ ስትሆን ስለአማጽያን ወታደሮቹ የተነገሩትን ሁሉንም አስፈሪ ገለጻዎች አምናቸዋለች፡፡ አንድ ምሽት ከመኝታ ቤቱ ውጪ ወደሚገኘው መታጠቢያ ክፍላችን ለመጠቀም ስሄድ ከእንቅልፏ ሳልቀሰቅሳት አልቀርም፡፡ ምሽቱ በጣም ይቀዘቅዝ ስለነበር እንዲሞቀኝ ትልቅ ፎጣዬን በራሴ አስሬ የሚረዝምብኝ የነበረ የሌሊት ልብስ ለብሻለሁ፡፡ ትንሽ ሳላስፈራ አልቀርም፣ ተመልሼ ለመግባት በሩን ለመክፈት ስሞክር ዳኒዳ ፊቴ ላይ በኃይል ዘጋችብኝ፡፡ ኡኡታዋን ስታቀልጠው ግቢው ተሸበረ፡፡
‹‹አድኑኝ! እርዱኝ! ወይኔ አምላኬ! ኧረ እርዱኝ፡፡ የሩአግ ወታደር ነው - ሊገድለን፣ ሊበላን መጣ፡፡ አቤት ቀንዶቹ!››
የዳኒዳን ጆሮ ሰንጥቆ የሚገባ ድምፅ ስላወቅሁት በእርጋታ ‹‹ዳኒዳ፣ እኔ እኮ ነኝ፣ ኢማኪዩሌ ነኝ፡፡ ወታደር አይደለሁም፡፡ ቀንድም የለኝ፤ ፎጣዬን ነው እኮ ራሴ ላይ ያሰርኩት!›› አልኳት፡፡
ሞቅ አድርገው የሚረግጡ እግሮች ከኮረኮንቹ ጎዳና በኩል ሰምቼ ዘወር ስል የትምህርት ቤታችን ትልቁ ዘበኛ በደረቴ ትይዩ ያነጣጠረ ጦር ይዞ በጨለማው ወደኔ ይገሰግሳል፡፡ ብርክ ይዞኝ ጉልበቴ ተሽመድምዶ መሬት ላይ ቁጭ አልኩ፡፡ ዘበኛው ከእኔ መጠነኛ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ! ኢማኪዩሌ፣ ገድዬሽ ነበር እኮ! ማናባቷ ነች እንደዚያ የምትጮኸው?›› አለ፡፡
በወቅቱ
፡
፡
#ምዕራፍ_ሦስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ቅድመ_ከፍተኛ_ትምህርት
በሦስተኛውና በመጨረሻው ዓመት ጦርነት ከመፈንዳቱ በቀር ሕይወት በሊሴ ጥሩ ነበር፡፡
የ1990 የጥቅምት ወር የመጀመሪያዋ ቀን ከሰዓት ቆንጆና ብሩህ ነበረች፡፡ የክፍል ጓደኞቼና እኔ የግብረገብ ትምህርት ክፍለጊዜያችን እስኪጀምር እየጠበቅን መምህሩ ለምን እንደዘገየ እናስባለን፡፡ አቶ ጋሂጊ ለመግባባት የማያስቸግር፣ የተረጋጋና ምናልባትም ካገኘኋቸው ሰዎች ሁሉ ልስልስ ጸባይ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም በመጨረሻ እጆቹን አያይዞ ሲመጣና በክፍሉ ፊትለፊት ወደፊትና ወደኋላ ሄድ መለስ ሲል አንዳች ነገር እንደተከሰተ ገምተናል፡፡ አንደኛዋ ተማሪ ችግሩ ምን እንደሆነ ብትጠይቀውም ወደ እኛ ሳያይ መለስ ቀለስ ማለቱን ቀጠለ፡፡
መምህራችን አንዳች መጥፎ ዜና እንደደበቀንና ምን አልባትም የተንቀሳቃሽ ምስል ትዕይንት ምሽትን መነኩሲቶቹ ሰርዘውት እንደሆነ ሊነግረን ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ጉዳዩ ግን ከዚያ የባሰ ነበር፡፡ በትምህርት ቤት ውስጥ የዜና ዘገባዎችን ማዳመጥ ስለማይፈቀድልን በመኖሪያ ቤቴ እንደነበረው ሁሉ ከዓለም ወሬ ተነጥያለሁ፡፡
‹‹በሀገሪቱ ላይ ጥቃት እንደተፈጸመ ሰማሁ›› ሲል አቶ ጋሂጊ በሃዘኔታ ነገረን፡፡ ‹‹በጣም አደገኛና በሁላችንም ላይ ለረጅም ጊዜ ተጽዕኖ የሚኖረው ይሆናል ብዬ እፈራለሁ፡፡››
ክፍሉ በጸጥታ ተዋጠ - ከዚያ ሁሉም ባንዴ ማውራት ጀመረ፣ ጥያቄ መጠያየቅ፣ ሩዋንዳን ማን ለምን እንደሚያጠቃት ለማወቅ መጠባበቅ፡፡
‹‹በዩጋንዳ የሚኖር የአማጽያን ቡድን የአገሪቱን ድንበር አቋርጧል›› ሲል መለሰልን፡፡ ‹‹በዋነኝነት ከሩዋንዳ የሄዱ ጥገኞች ልጆች ሲሆኑ ተሰባስበው ወደ ሀገሪቱ ለመግባት እየተዋጉ ነው፡፡ ከዚህ ስፍራ በስተሰሜን በኩል በአሁኑ ሰዓት በአማጽያንና በሩዋንዳ መንግሥት ወታደሮች መካከል ከባድ ውጊያ በመካሄድ ላይ ነው፡፡›› አቶ ጋሂጊ ፍርሃትና ንዴትን የሚያንጸባርቅ የጥያቄዎች ዝናብ ወረደበት፡፡ ‹‹ቱትሲዎቹ ሽፍቶች ግን ምንድን ነው የሚፈልጉት? ለምን ጦርነት ይከፍቱብናል? ትምህርት ቤቱ ጋር ከደረሱስ ምን ያደርጉን ይሆን?››
የሃፍረት ሙቀት በማጅራቴ ተሰማኝ፤ በማስደገፊያዬም ስር ለመደበቅ ፈለግሁ፡፡ በክፍሉ ውስጥ ካለነው 50 ተማሪዎች 47ቱ ሁቱዎች ናቸው፡፡ በጣም ስለፈራሁና ስለራሴ ስለተጨነቅሁ ሌሎቹን ሁለት ቱትሲ ልጃገረዶች ማየት እንኳን ተሳነኝ፡፡ በቱትሲነቴ ሳፍርና በሊሴም ተለይቼ ስታይ የመጀመሪያዬ ነው፡፡
‹‹አማጽያኑ ራሳቸውን የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር (ሩአግ) ብለው አደራጅተዋል፡፡ ቡድኑ ሩዋንዳን ከዓመታት በፊት ለቀው የሄዱና እንዳይመለሱ የተከለከሉ የቱትሲዎች ድርጅት ነው፡፡ እነዚህ የውጪ ዜጎች ወደ ሩዋንዳ በመግባት መንግሥታዊውን ለመያዝ ጦርነት አውጀውብናል›› አለ፡፡
ስለ ሩአግ ምንነት ግንዛቤው ነበረኝ፡፡ አባላቱ መንግሥትን ለመጣል ሲሉ ብቻ እንደማይዋጉም አውቃለሁ፡፡ እኩልነት በሰፈነባትና በነጻ ሀገር መኖርን ይፈልጋሉ፡፡ አብዛኞቹ የሩአግ ወታደሮች ስደተኞች ቱትሲዎች ወይንም ልጆቻቸው ናቸው፡፡
በ1959ና በ1973ቱ ችግሮች እንዲሁም ሁቱ ጽንፈኞች የግድያ ዘመቻዎችን ባካሄዱባቸው ሌሎች በርካታ ጊዜያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሕይወት ለማዳን ከሩዋንዳ ሸሽተዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ አማጽያኑን ‹‹የውጪ ዜጎች›› ያላቸው አብዛኞቹ እንደ ዩጋንዳና ዛየር ባሉ ጎረቤት ሀገራት ስላደጉ ነው - ያ የሆነው ግን ርዕሰ-ብሔር ሃብያሪማና ስደተኞች ፈጽሞ ወደ ሀገራቸው አንዳይመለሱ የሚከለክል ሕግ ስላወጡ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ግዙፍ የቱትሲ ስደተኞች ስብስብ እንዲፈጠር ያደረጉ ሲሆን አንድ ሙሉ የሩዋንዳ ቱትሲዎች ትውልድንም አንዴ እንኳን የእናት አገሩን አፈር ሳይረግጥ እንዲያድግ አስገድደዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ ያንን ፈጽሞ ባይገልጽም ቱትሲዎች ራሳቸውን ከጽንፈኛ ሁቱዎች ለመከላከል በሞከሩ ቁጥር ግን ምን እንደሚከሰት ያውቃል፡፡ ለእኛ መጨነቁን ‹‹ይህ ለቱትሲዎች በጣም አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል - ይህን ዓይነት ነገር ወደ ብዙ ግድያዎች ሊያመራ ስለሚችል መንግሥትና አማጽያኑ ችግራቸውን እንዲፈቱና ደም መፋሰስ እንዲቆም እንጸልይ፡፡››
የዕለቱ ትምህርታችን በዚሁ አበቃ፡፡ ሴቶቹ ልጆች ግን የሚያወሩት ስለጥቃቱና ቱትሲ ወታደሮቹ ወደ ትምህርት ቤታችን ቢደርሱ ምን ማድረግ እንደሚኖርባቸው ብቻ ሆነ፡፡ ከሁለት ቱትሲ የክፍል ጓደኞቼ ጋር ጸጥ ብዬ ላለመታየት እየሞከርኩ ተቀመጥሁ፡፡ ቱትሲዎች እንዴት ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደተያዙ ሳስብ ሃፍረቴ ወደ ንዴት ተለወጠ፡፡ የመንግሥት ወታደሮችን አሸንፎ ለመድሎው ፍጻሜ ያበጅለት ዘንድ ተስፋ በማድረግ በልቤ ለሩአግ አጋርነቴን አሳየሁ፡፡ በመጨረሻ ግን ንዴቴ ወደ ፍራቻ የተቀየረው ስለመንደሬና ስለቤተሰቤ በተጨነቅሁ ጊዜ ነው፡፡ አምላኬ ቤተሰቤን ሰላም ያደርግልኝ ዘንድ ዓይኖቼን ጨፍኜ ተማጸንኩት - በወቅቱ ያለ-ነሱ እንዴት በሕይወት እንደምቆይ ስለማላውቅ፡፡
ብዙዎቹ ተማሪዎች ጦርነቱ አስከፊ በነበረበት በሰሜኑ ክፍል ዘመዶች ስለነበሯቸው የትምህርት ቤቱ ርዕሰ - መምህር የሬድዮ ዘገባ እንድናዳምጥና ስለ ክስተቱ እንድንረዳ ፈቀደልን፡፡ ብሄራዊው ሬድዮ የሚያስተላልፈው ዘገባ ከሞላ ጎደል የጥላቻ ውትወታ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዘጋቢዎቹ አማጽያኑ እንደ አውሬ በጫካ እንደሚኖሩ፣ የሰው ስጋ እንደሚበሉና ከዝንጀሮዎች ጋር ወሲብ እንደሚፈጽሙ አተቱ፡፡ የለየላቸው ሰይጣኖች ስለሆኑ ቀንድ አብቅለዋል ተባለ፡፡ ‹‹አማጽያን በረሮዎቹ›› በማናቸውም ስፍራና ጊዜ ሊተናኮሉ ስለሚችሉና መሰሪ ስለሆኑ ሩዋንዳውያን ራሳቸውን እንዲጠብቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው፡፡ እነዚህ ዘገባዎች ቀድሞውንም የተዛባ አመለካከት የነበራቸውን ልጃገረዶች አቀጣጠሏቸው፡፡ አንዷማ በጣም ፈርታ ስለነበር ልታስገድለኝ ነበር፡፡
ዳኒዳ ከመኝታ ቤት እህቶቼ አንዷ ስትሆን ስለአማጽያን ወታደሮቹ የተነገሩትን ሁሉንም አስፈሪ ገለጻዎች አምናቸዋለች፡፡ አንድ ምሽት ከመኝታ ቤቱ ውጪ ወደሚገኘው መታጠቢያ ክፍላችን ለመጠቀም ስሄድ ከእንቅልፏ ሳልቀሰቅሳት አልቀርም፡፡ ምሽቱ በጣም ይቀዘቅዝ ስለነበር እንዲሞቀኝ ትልቅ ፎጣዬን በራሴ አስሬ የሚረዝምብኝ የነበረ የሌሊት ልብስ ለብሻለሁ፡፡ ትንሽ ሳላስፈራ አልቀርም፣ ተመልሼ ለመግባት በሩን ለመክፈት ስሞክር ዳኒዳ ፊቴ ላይ በኃይል ዘጋችብኝ፡፡ ኡኡታዋን ስታቀልጠው ግቢው ተሸበረ፡፡
‹‹አድኑኝ! እርዱኝ! ወይኔ አምላኬ! ኧረ እርዱኝ፡፡ የሩአግ ወታደር ነው - ሊገድለን፣ ሊበላን መጣ፡፡ አቤት ቀንዶቹ!››
የዳኒዳን ጆሮ ሰንጥቆ የሚገባ ድምፅ ስላወቅሁት በእርጋታ ‹‹ዳኒዳ፣ እኔ እኮ ነኝ፣ ኢማኪዩሌ ነኝ፡፡ ወታደር አይደለሁም፡፡ ቀንድም የለኝ፤ ፎጣዬን ነው እኮ ራሴ ላይ ያሰርኩት!›› አልኳት፡፡
ሞቅ አድርገው የሚረግጡ እግሮች ከኮረኮንቹ ጎዳና በኩል ሰምቼ ዘወር ስል የትምህርት ቤታችን ትልቁ ዘበኛ በደረቴ ትይዩ ያነጣጠረ ጦር ይዞ በጨለማው ወደኔ ይገሰግሳል፡፡ ብርክ ይዞኝ ጉልበቴ ተሽመድምዶ መሬት ላይ ቁጭ አልኩ፡፡ ዘበኛው ከእኔ መጠነኛ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ! ኢማኪዩሌ፣ ገድዬሽ ነበር እኮ! ማናባቷ ነች እንደዚያ የምትጮኸው?›› አለ፡፡
በወቅቱ
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ዩኒቨርሲቲ
፡
በ1991 ክረምት መጨረሻ የማይቻለው ተከሰተ - በቡታሬ በሚገኘው ብሄራዊው ዩኒቨርሲቲ መማር የሚያስችለኝ የትምህርት ዕድል ተሰጠኝ፡፡ በሕይወቴ ሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትን በጽኑ ስመኝ ነበር፡፡ በመሆኑም በፊቴ እነዚያ ሁሉ መሰናክሎች ቢጋረጡብኝም በድንገት ሕልሜ እውን ሆነ፡፡
ወላጆቼ ዜናውን ሲሰሙ በጣም ተደስተው ተቁነጠነጡ፡፡ በትክክለኛው የሩዋንዳ ደንብ - ያው በድግስ መሆኑ ነው - እናከብረው ዘንድም ምግብና መጠጥ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ይሉ ጀመር፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከቤታችን የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ነሽ፣ ስለሆነም አሁኑኑ ይህን ለሁሉም ሰው ማሳወቅ አለብን!›› ሲል አባቴ በኩራት ተናገረ፡፡ በማግስቱ ረጅም መንገድ ተጉዤ ለአያቴ፣ ለአክስቶቼ፣ ለአጎቶቼና ለሁሉም በአቅራቢያችን መንደሮች ለሚኖሩት ልጆቻቸው ወሬውን እንዳበስር አመቻቸልኝ፡፡
ሌሊቱን ሙሉ ስንስቅ፣ ስንበላና ወደፊት ስለሚኖሩት በጎ ነገሮች ሁሉ ስናወጋ አሳለፍን፡፡ ወላጆቼ በዚያ ምሽት ሸክም ከትከሻዎቸው እንደወረደላቸው ሁሉ ወደ ወጣትነት የተመለሱ መሰሉኝ፡፡
እናቴ በደስታ ፈክታ አመሸች፡፡ ‹‹ሁሉም ነገር ላንቺ ብሩህ የሆነልሽ ይመስላል፣ ኢማኪዩሌ›› አለችኝ፡፡ ‹‹ከአሁን በኋላ ሙሉ በሙሉ የራስሽን መንገድ ማበጀት ትችያለሽ፤ ቀና በይ፤ ማንም ሌላ ሰው በገበታሽ ላይ በፍጹም ምግብ እንዲያስቀምጥልሽ አትጠባበቂ፡፡››
አባቴም ከኔ ጋር መጠጫ አጋጭቶ ብዙ አባታዊ ምክር ለገሰኝ፡፡ ‹‹ብዙውን ጊዜ በዩኒቨርሲቲ የሚማሩት ወንዶች ሲሆኑ እነርሱም አንቺን እንደነርሱ ጎበዝ ነች ብለው አያስቡም፡፡ ግን እንደነሱ መትጋት እንደምትችዪ አውቃለሁ፤ አንዲያውም ከማንኛውም ወንድ በተሻለ፡፡ አንቺ ቱትሲ ስለሆንሽ ዩኒቨርሲቲ መግባት ፈተና ሆኖብሽ ቆይቷል፤ ይኸው አስቸጋሪው ወቅት አለፈ፡፡ እንግዲህ የራስሽ ድርሻ ነው - በደንብ አጥኚ፣ ጸልዪ፤ ስታድጊ በስስት እናይሽ እንደነበርሽው ምስጉን፣ ደግና ቆንጆ ልጅ መሆንሽን ቀጥዪበት፡፡››
በጣፋጭና ፍቅር የተሞላባቸው ቃላቱ ልቤ ሐሴት አደረገች፡፡ ‹‹ሃሳብ አይግባህ አባባ›› አልኩት፡፡ ‹‹አንተንም ሆነ እማማን አላሳፍራችሁም፡፡ አኮራችኋለሁ፡፡››
ስለ ሰው ልቦናና አእምሮ አሠራር ለመማር ሥነ ልቦናንና ፍልስፍናን ለማጥናት ብፈልግም የትምህርት ዕድሉ በተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች ባሉ ክፍት ቦታዎች የተወሰነ ስለነበር ራሴ የምፈልገውን የጥናት መስክ እንድመርጥ አልተፈቀደልኝም፡፡ በተግባራዊ ሳይንስ መርሃ-ግብር መመደቤ ተስማምቶኛል፡፡ በሊሴ ለወንድሞቼ ችሎታዬን ለማሳየት ስል ራሴን በሒሳብና ፊዚክስ አብቅቼ ስለነበር አሁን ያ ሥንቅ ይሆነኛል፡፡ ሻንጣዎቼን አዘገጃጅቼ ወዲያውኑ ከመንደሬ ደቡብ ምሥራቅ አራት ሰዓት ወደሚያስነዳውና ፍጹም አዲስ ሕይወት ወደሚጠብቀኝ ወደ ቡታሬ አቀናሁ፡፡
ትምህርት ቤቱ ቅጥር-ግቢ ስደርስ ክሌሜንታይንን ጨምሮ ከሊሴ ስድስቱ የሴት ጓደኞቼ፣ የትምህርት ዕድሉን ማግኘታቸውን ተረዳሁ፡፡ ጓደኛዬ ሳራ እዚያው አንድ ዓመት ቀድማ ገብታ ስትማር የቆየች ሲሆን አንድ መኝታ ክፍል ውስጥ አብረን እንድንኖር ስትጠብቀኝ ኖሯል፡፡ በተጨናነቁ ክፍሎች ውስጥ ከተኛሁባቸው ከእነዚያ ዓመታት በኋላ ከአንዲት ሴት ልጅ ጋር ብቻ አንድ ክፍል መጋራት እጅግ ይመቻል፡፡ ክሌሜንታይን ብዙ ጊዜ የኛን ክፍል ትጎበኝ የነበረ ሲሆን በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን ራሳችንን በኤሌክትሪክ የማቃጠሉን ዕቅዳችንን ባለመፈጸማችን እንዴት ዕድለኞች እንደነበርን በጨዋታ መካከል እናነሳለን፡፡ ያ ቢሆን ኖሮ የዩኒቨርሲቲን አስደሳች ነገሮች ሁሉ መች እናይ ነበር?
ትምህርቱን ወደድኩት፤ በጣም ጠንክሬም አጠና ጀመር፡፡ የዩኒቨርሲቲን አስደሳችነትና ነጻነት እንዴት እንደወደድኩት! የትምህርት ዕድሉ ለእኔ ትልቅ ነገር የነበረውን ወደ 30 የአሜሪካን ዶላር የሚሆን ወርሃዊ የኪስ ገንዘብንም ይጨምራል፡፡ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ትልቅ ሰው ነጻነት ተሰማኝ፡፡ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ መልበስ ቀረልኝ፤ ከተማም ሄድ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር ቆንጆ ቆንጆ ልብሶችን መግዛት ቻልኩ፡፡ አቤት ሲያስደስት!
ቡና ተፈልቶ በሚሸጥባቸው ስፍራዎች፣ በሰንበት ተንቀሳቃሽ ምስል በሚታይባቸው ቦታዎችና በየአሥራ አምስት ቀኑ ቅዳሜ ምሽት በሚካሄዱት የትምህርት ቤት አቀፍ የዳንኪራ ጊዜያት እስከመገኘት ደርሼ በማኅበራዊ ሕይወት በጣም ንቁ ተሳታፊ ሆንኩ፡፡ የትዕይንት ማሳያ ቡድንንም ተቀላቅዬ ብዙውን ጊዜ የቡታሬ ከንቲባ በሚገኙባቸው በሁሉም ትዕይንቶች እዘፍንና እጨፍር ነበር፡፡ ሃይማኖታዊ ገጸባህርያትን ወክሎ መተወን ምርጫዬ በመሆኑ እንዲያውም አንድ ጊዜ የምወዳትን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወክዬ ተጫውቻለሁ፡፡ ሁልጊዜ ለጸሎት የሚሆን ጊዜ እተዋለሁ፡፡ ያንን ጽናት ማግኘቴና ጸሎት ማድረጌ እጅጉን አረጋግቶኝና አትኩሮቴን እንድሰበስብ ረድቶኝ ነበር፡፡ ቤተ-ክርስቲያን በሳምንት ብዙ ጊዜ እሄዳለሁ፤ ከሴት ጓደኞቼም ጋር የጸሎት ቡድን አቋቁሜያለሁ፡፡
ለናፍቆት ጊዜ ባይኖረኝም ከአባቴ የሚላኩልኝ ብቸኝነት የሚንጸባረቅባቸው ደብዳቤዎች ቤተሰቤን ቶሎ ቶሎ መጎብኘት እንዳለብኝ አስገነዘቡኝ፡፡ በወቅቱ ቪያኒ በአዳሪ ትምህርት ቤት ስለነበር ወላጆቼ ብቸኝነትን መላመድ አቅቷቸዋል፡፡ ‹‹ከልጆቼ አንዳቸውም እዚህ ሳይኖሩ ሕይወቴ እንደ ዱሮው ሊሆን አይችልም›› ሲል አባቴ ጻፈልኝ፡፡ ‹‹ቤቱ በጣም ጭር ብሏል፡፡ አንዳንዴ እኔና እናትሽ እርስ በርሳችን እንተያይና እንገረማለን፣ ‹ያ ሁሉ ሣቅ የት ሄደ?› እንላለን፡፡ የራስሽ ልጆች ሲኖሩሽ፣ ኢማኪዩሌ፣ ሳትጠግቢያቸው ስለሚሄዱብሽ አብረውሽ እያሉ እያንዳንዷን ደቂቃ በደስታ ማሳለፍሽን እርግጠኛ ሁኚ፣ …››
በማታባ ያሉትን የተወሰኑትን ጓደኞቼን የሚያውቅ ዮሃንስ የሚባል ተማሪ ጓደኛም አገኘሁ፡፡ ከእኔ ሦስት ዓመት ይበልጥ የነበረና ‹‹ድንገት›› ከኔ ጋር በትምህርት ቤቱ የተለያዩ ስፍራዎች ግጥምጥም የማለት የተለየ ጸባይ የነበረው ልጅ ነው፡፡ መጽሐፍቴን ይይዝልኝ፣ የትምህርት ቤታችንን ግቢ ያሳየኝና ከጓደኞቹ ጋር ያስተዋውቀኝ ጀመር፡፡ አማላይ፣ ታጋሽና ለሰው አሳቢ ልጅ ነበር፡፡ በጫካው ውስጥ ለረጅም የእግር ጉዞ አብረን እየሄድን ለእኛ አስፈላጊ ስለሆነው ጉዳይ እናወራለን - ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ ቤተሰብና ስለ ጥሩ ትምህርት፡፡ በኋላም ላይ ፍቅር ለመጀመር በቃን፤ በመጭዎቹም ዓመታት ውስጥ አንዳችን ለሌላችን በጣም እንተሳሰብ ጀመር፡፡ ዮሃንስ ሁቱ ቢሆንም ግን ይህ ጭራሽ ጉዳያችን አልነበረም፡፡ ለአባቴ ይልቁን ዮሃንስ ወንጌላዊ ክርስቲያንና የሰባኪ ልጅ መሆኑ ያሳስበዋል፡፡
‹‹ካቶሊክ መሆንሽን አትርሺ›› እያለ አባቴ ያስታውሰኛል፡፡ ‹‹ዮሃንስ ጥሩ ልጅ ይመስላል፤ እንድታፈቅሪውም መርቄሻለሁ - ግን ወደ እርሱ ኃይማኖት ሊቀይርሽ እስካልሞከረ ድረስ ነው፡፡›› አባቴ በጣም ታጋሽ ሰው ሲሆን ሃይማኖተኛም ነው በዩኒቨርሲቲ የቆየሁባቸው ሁለቱ የመጀመሪያ ዓመታት በረሩ፤ ሁሉም ነገር መልካም ሆነልኝ - ውጤቴ ጥሩ፣ ቤተሰቤ ጤነኛ፣ ሕይወቴም አስደሳች ሕይወት ስለሚመች አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ጦርነት መኖሩን ለመርሳት አይከብደንም፡፡ አልፎ አልፎ የሚካሄዱ የሰላም ድርድሮችና የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢኖሩም በቱትሲ አማጽያንና በመንግሥት
፡
፡
#ምዕራፍ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ዩኒቨርሲቲ
፡
በ1991 ክረምት መጨረሻ የማይቻለው ተከሰተ - በቡታሬ በሚገኘው ብሄራዊው ዩኒቨርሲቲ መማር የሚያስችለኝ የትምህርት ዕድል ተሰጠኝ፡፡ በሕይወቴ ሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትን በጽኑ ስመኝ ነበር፡፡ በመሆኑም በፊቴ እነዚያ ሁሉ መሰናክሎች ቢጋረጡብኝም በድንገት ሕልሜ እውን ሆነ፡፡
ወላጆቼ ዜናውን ሲሰሙ በጣም ተደስተው ተቁነጠነጡ፡፡ በትክክለኛው የሩዋንዳ ደንብ - ያው በድግስ መሆኑ ነው - እናከብረው ዘንድም ምግብና መጠጥ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ይሉ ጀመር፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከቤታችን የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ነሽ፣ ስለሆነም አሁኑኑ ይህን ለሁሉም ሰው ማሳወቅ አለብን!›› ሲል አባቴ በኩራት ተናገረ፡፡ በማግስቱ ረጅም መንገድ ተጉዤ ለአያቴ፣ ለአክስቶቼ፣ ለአጎቶቼና ለሁሉም በአቅራቢያችን መንደሮች ለሚኖሩት ልጆቻቸው ወሬውን እንዳበስር አመቻቸልኝ፡፡
ሌሊቱን ሙሉ ስንስቅ፣ ስንበላና ወደፊት ስለሚኖሩት በጎ ነገሮች ሁሉ ስናወጋ አሳለፍን፡፡ ወላጆቼ በዚያ ምሽት ሸክም ከትከሻዎቸው እንደወረደላቸው ሁሉ ወደ ወጣትነት የተመለሱ መሰሉኝ፡፡
እናቴ በደስታ ፈክታ አመሸች፡፡ ‹‹ሁሉም ነገር ላንቺ ብሩህ የሆነልሽ ይመስላል፣ ኢማኪዩሌ›› አለችኝ፡፡ ‹‹ከአሁን በኋላ ሙሉ በሙሉ የራስሽን መንገድ ማበጀት ትችያለሽ፤ ቀና በይ፤ ማንም ሌላ ሰው በገበታሽ ላይ በፍጹም ምግብ እንዲያስቀምጥልሽ አትጠባበቂ፡፡››
አባቴም ከኔ ጋር መጠጫ አጋጭቶ ብዙ አባታዊ ምክር ለገሰኝ፡፡ ‹‹ብዙውን ጊዜ በዩኒቨርሲቲ የሚማሩት ወንዶች ሲሆኑ እነርሱም አንቺን እንደነርሱ ጎበዝ ነች ብለው አያስቡም፡፡ ግን እንደነሱ መትጋት እንደምትችዪ አውቃለሁ፤ አንዲያውም ከማንኛውም ወንድ በተሻለ፡፡ አንቺ ቱትሲ ስለሆንሽ ዩኒቨርሲቲ መግባት ፈተና ሆኖብሽ ቆይቷል፤ ይኸው አስቸጋሪው ወቅት አለፈ፡፡ እንግዲህ የራስሽ ድርሻ ነው - በደንብ አጥኚ፣ ጸልዪ፤ ስታድጊ በስስት እናይሽ እንደነበርሽው ምስጉን፣ ደግና ቆንጆ ልጅ መሆንሽን ቀጥዪበት፡፡››
በጣፋጭና ፍቅር የተሞላባቸው ቃላቱ ልቤ ሐሴት አደረገች፡፡ ‹‹ሃሳብ አይግባህ አባባ›› አልኩት፡፡ ‹‹አንተንም ሆነ እማማን አላሳፍራችሁም፡፡ አኮራችኋለሁ፡፡››
ስለ ሰው ልቦናና አእምሮ አሠራር ለመማር ሥነ ልቦናንና ፍልስፍናን ለማጥናት ብፈልግም የትምህርት ዕድሉ በተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች ባሉ ክፍት ቦታዎች የተወሰነ ስለነበር ራሴ የምፈልገውን የጥናት መስክ እንድመርጥ አልተፈቀደልኝም፡፡ በተግባራዊ ሳይንስ መርሃ-ግብር መመደቤ ተስማምቶኛል፡፡ በሊሴ ለወንድሞቼ ችሎታዬን ለማሳየት ስል ራሴን በሒሳብና ፊዚክስ አብቅቼ ስለነበር አሁን ያ ሥንቅ ይሆነኛል፡፡ ሻንጣዎቼን አዘገጃጅቼ ወዲያውኑ ከመንደሬ ደቡብ ምሥራቅ አራት ሰዓት ወደሚያስነዳውና ፍጹም አዲስ ሕይወት ወደሚጠብቀኝ ወደ ቡታሬ አቀናሁ፡፡
ትምህርት ቤቱ ቅጥር-ግቢ ስደርስ ክሌሜንታይንን ጨምሮ ከሊሴ ስድስቱ የሴት ጓደኞቼ፣ የትምህርት ዕድሉን ማግኘታቸውን ተረዳሁ፡፡ ጓደኛዬ ሳራ እዚያው አንድ ዓመት ቀድማ ገብታ ስትማር የቆየች ሲሆን አንድ መኝታ ክፍል ውስጥ አብረን እንድንኖር ስትጠብቀኝ ኖሯል፡፡ በተጨናነቁ ክፍሎች ውስጥ ከተኛሁባቸው ከእነዚያ ዓመታት በኋላ ከአንዲት ሴት ልጅ ጋር ብቻ አንድ ክፍል መጋራት እጅግ ይመቻል፡፡ ክሌሜንታይን ብዙ ጊዜ የኛን ክፍል ትጎበኝ የነበረ ሲሆን በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን ራሳችንን በኤሌክትሪክ የማቃጠሉን ዕቅዳችንን ባለመፈጸማችን እንዴት ዕድለኞች እንደነበርን በጨዋታ መካከል እናነሳለን፡፡ ያ ቢሆን ኖሮ የዩኒቨርሲቲን አስደሳች ነገሮች ሁሉ መች እናይ ነበር?
ትምህርቱን ወደድኩት፤ በጣም ጠንክሬም አጠና ጀመር፡፡ የዩኒቨርሲቲን አስደሳችነትና ነጻነት እንዴት እንደወደድኩት! የትምህርት ዕድሉ ለእኔ ትልቅ ነገር የነበረውን ወደ 30 የአሜሪካን ዶላር የሚሆን ወርሃዊ የኪስ ገንዘብንም ይጨምራል፡፡ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ትልቅ ሰው ነጻነት ተሰማኝ፡፡ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ መልበስ ቀረልኝ፤ ከተማም ሄድ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር ቆንጆ ቆንጆ ልብሶችን መግዛት ቻልኩ፡፡ አቤት ሲያስደስት!
ቡና ተፈልቶ በሚሸጥባቸው ስፍራዎች፣ በሰንበት ተንቀሳቃሽ ምስል በሚታይባቸው ቦታዎችና በየአሥራ አምስት ቀኑ ቅዳሜ ምሽት በሚካሄዱት የትምህርት ቤት አቀፍ የዳንኪራ ጊዜያት እስከመገኘት ደርሼ በማኅበራዊ ሕይወት በጣም ንቁ ተሳታፊ ሆንኩ፡፡ የትዕይንት ማሳያ ቡድንንም ተቀላቅዬ ብዙውን ጊዜ የቡታሬ ከንቲባ በሚገኙባቸው በሁሉም ትዕይንቶች እዘፍንና እጨፍር ነበር፡፡ ሃይማኖታዊ ገጸባህርያትን ወክሎ መተወን ምርጫዬ በመሆኑ እንዲያውም አንድ ጊዜ የምወዳትን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወክዬ ተጫውቻለሁ፡፡ ሁልጊዜ ለጸሎት የሚሆን ጊዜ እተዋለሁ፡፡ ያንን ጽናት ማግኘቴና ጸሎት ማድረጌ እጅጉን አረጋግቶኝና አትኩሮቴን እንድሰበስብ ረድቶኝ ነበር፡፡ ቤተ-ክርስቲያን በሳምንት ብዙ ጊዜ እሄዳለሁ፤ ከሴት ጓደኞቼም ጋር የጸሎት ቡድን አቋቁሜያለሁ፡፡
ለናፍቆት ጊዜ ባይኖረኝም ከአባቴ የሚላኩልኝ ብቸኝነት የሚንጸባረቅባቸው ደብዳቤዎች ቤተሰቤን ቶሎ ቶሎ መጎብኘት እንዳለብኝ አስገነዘቡኝ፡፡ በወቅቱ ቪያኒ በአዳሪ ትምህርት ቤት ስለነበር ወላጆቼ ብቸኝነትን መላመድ አቅቷቸዋል፡፡ ‹‹ከልጆቼ አንዳቸውም እዚህ ሳይኖሩ ሕይወቴ እንደ ዱሮው ሊሆን አይችልም›› ሲል አባቴ ጻፈልኝ፡፡ ‹‹ቤቱ በጣም ጭር ብሏል፡፡ አንዳንዴ እኔና እናትሽ እርስ በርሳችን እንተያይና እንገረማለን፣ ‹ያ ሁሉ ሣቅ የት ሄደ?› እንላለን፡፡ የራስሽ ልጆች ሲኖሩሽ፣ ኢማኪዩሌ፣ ሳትጠግቢያቸው ስለሚሄዱብሽ አብረውሽ እያሉ እያንዳንዷን ደቂቃ በደስታ ማሳለፍሽን እርግጠኛ ሁኚ፣ …››
በማታባ ያሉትን የተወሰኑትን ጓደኞቼን የሚያውቅ ዮሃንስ የሚባል ተማሪ ጓደኛም አገኘሁ፡፡ ከእኔ ሦስት ዓመት ይበልጥ የነበረና ‹‹ድንገት›› ከኔ ጋር በትምህርት ቤቱ የተለያዩ ስፍራዎች ግጥምጥም የማለት የተለየ ጸባይ የነበረው ልጅ ነው፡፡ መጽሐፍቴን ይይዝልኝ፣ የትምህርት ቤታችንን ግቢ ያሳየኝና ከጓደኞቹ ጋር ያስተዋውቀኝ ጀመር፡፡ አማላይ፣ ታጋሽና ለሰው አሳቢ ልጅ ነበር፡፡ በጫካው ውስጥ ለረጅም የእግር ጉዞ አብረን እየሄድን ለእኛ አስፈላጊ ስለሆነው ጉዳይ እናወራለን - ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ ቤተሰብና ስለ ጥሩ ትምህርት፡፡ በኋላም ላይ ፍቅር ለመጀመር በቃን፤ በመጭዎቹም ዓመታት ውስጥ አንዳችን ለሌላችን በጣም እንተሳሰብ ጀመር፡፡ ዮሃንስ ሁቱ ቢሆንም ግን ይህ ጭራሽ ጉዳያችን አልነበረም፡፡ ለአባቴ ይልቁን ዮሃንስ ወንጌላዊ ክርስቲያንና የሰባኪ ልጅ መሆኑ ያሳስበዋል፡፡
‹‹ካቶሊክ መሆንሽን አትርሺ›› እያለ አባቴ ያስታውሰኛል፡፡ ‹‹ዮሃንስ ጥሩ ልጅ ይመስላል፤ እንድታፈቅሪውም መርቄሻለሁ - ግን ወደ እርሱ ኃይማኖት ሊቀይርሽ እስካልሞከረ ድረስ ነው፡፡›› አባቴ በጣም ታጋሽ ሰው ሲሆን ሃይማኖተኛም ነው በዩኒቨርሲቲ የቆየሁባቸው ሁለቱ የመጀመሪያ ዓመታት በረሩ፤ ሁሉም ነገር መልካም ሆነልኝ - ውጤቴ ጥሩ፣ ቤተሰቤ ጤነኛ፣ ሕይወቴም አስደሳች ሕይወት ስለሚመች አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ጦርነት መኖሩን ለመርሳት አይከብደንም፡፡ አልፎ አልፎ የሚካሄዱ የሰላም ድርድሮችና የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢኖሩም በቱትሲ አማጽያንና በመንግሥት
👍1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ሀገር_ቤት
፡
ሁልጊዜ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ የጥላቻ ድምፅ እሰማለሁ፡፡ የአር.ቲ. ኤል. ኤም. ሬድዮ የጥላቻ ድምጾች በመኝታ ቤቴ መስኮት ገብተው ህልሞቼ ውስጥ እስኪደነቀሩ ሌሊቱን በሰላም ተኝቼ አሳልፋለሁ፡፡ ልብ ይበሉ፣ በሦስተኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ አር. ቲ. ኤል. ኤም. በጽንፈኛ ሁቱዎች ዘንድ አዲሱና በጣም ታዋቂው ሬድዮ ጣቢያ ለመሆን ችሏል፡፡ ጸረ-ቱትሲ መርዝን የሚረጭ የተለየ የጥላቻ መሣሪያ ወጥቶታል፡፡
ሁሌ ‹‹ስለ ሁቱ የበላይነት›› የሚጮህ አካል-አልባ ክፉ ድምፅ ሆነ፡፡ የሁቱ የበላይነትም ሁቱዎችን በቱትሲ ወዳጆቻቸውና ጎረቤቶቻቸው ላይ እንዲነሱ የሚያደርግ ተናዳፊ ተርብ ለመሆን ቻለ፡፡ ‹‹እነዚያ በረሮ ቱትሲዎች ሊገድሉን ወጥተዋል፡፡ አትመኗቸው… እኛ ሁቱዎች ቀድመናቸው ልንነሳ ይገባናል! መንግሥታችንን ገልብጠው ሊያሳድዱን እየዶለቱብን ነው፡፡ በርዕሰ-ብሔራችን ላይ አንዳች ነገር ቢከሰት ሁሉንም ቱትሲዎች ወዲያውኑ ማውደም ግድ ይለናል! እያንዳንዱ ሁቱ ሩዋንዳን ከነዚህ ቱትሲ በረሮዎች ለማጽዳት እጅ ለእጅ መያያዝ
አለበት! የሁቱ የበላይነት! የሁቱ የበላይነት!››
ይህን በመሰለ አጉለኛ ሁኔታ ከእንቅልፌ እነቃለሁ፡፡ በእርግጥ ዘገባዎቹ እጅጉን በሚያስጠላ ሁኔታ እንጭጭ በመሆናቸው አልፎ አልፎ ያሥቃሉ፡፡ እነዚያን የልጅ ስድቦችና ልቅ ማስፈራሪያዎች ማንም ሰው ከምር ይቀበላቸዋል ብሎ ማመን አሰቸጋሪ ሲሆን መንግሥቱም የሕዝብ ንብረት የሆነውን የአየር ሰዓት ቱትሲዎችን ለማስፈራሪያ መፍቀዱን ማወቁ ይረብሻል፡፡ በወቅቱ ግን በሀገሪቱ በርካታ ስፍራዎች ቱትሲዎች በጽንፈኞች እየተገደሉ መሆኑን በሚገልጹ ወሬዎች ይበልጡን ተረበሽኩ፡፡ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እንዳሉት ጓደኞቼ ሁሉ በመገናኛ ብዙሃን ስለሚተላለፉት ዘገባዎች ብዙ ላለማሰብና ላለማውራት ሞከርኩ፡፡ ቤተሰቤ ሁሌ አስደሳችና ልዩ ጊዜ የሚያሳልፍበት የትንሣኤ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ ይህን የበዓል ወቅት ጎረቤቶቻችንን በመጋበዝና ወዳጅ-ዘመዶቻችንን በመጠየቅ እቤታችን እናሳልፋለን፡፡ የቤተሰቡ አባላት በሙሉ የምንገናኝበትን የትንሣኤን በዓል እቤቴ ማሳለፍ አምልጦኝ የማያውቅ ቢሆንም እየቀረቡ መጥተው ለነበሩት ፈተናዎቼ ለመዘጋጀት ያግዘኝ ዘንድ በትምህርት ቤቱ ለመቆየት ፈለግሁ፡፡ በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት ቆርጫለሁ፡፡ ወላጆቼ ስልክ ስላልነበራቸው ለአባቴ ለምን እቤት እንደማልሄድ የሚያብራራ ደብዳቤ ጻፍኩለት፡፡ ወላጆቼ ሁልጊዜ ልጆቻቸው የተሻለ ውጤት ያመጡ ዘንድ
ከሚጠበቀው በላይ እንዲያጠኑ ስለሚፈልጉ ቅር እንደማይሰኙብኝ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይህ ለካ ትልቅ ስህተት ኖሯል!
አባቴ እቤት እንድሄድ የሚለምን ደብዳቤ ጻፈልኝ፡፡ እንዲያውም የጠየቀኝ የትምህርት ቤት እረፍቴ እስኪደርስ ሳልጠብቅ ወዲያውኑ እንድሄድ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንድሆን እንደሚፈልግና እቤት ያላንዳች ረብሻ ማጥናት እንደሚቻለኝ ቃል ገባልኝ፡፡ ልባዊ ተማጽኖው በዓይኖቼ እንባ ሞላባቸው፡፡ ውድ ልጄ፣
ትምህርት አንቺን ከኛ እንደነጠቀን ይሰማኛል፡፡ እናትሽና እኔ እረፍትሽ እስኪጀምር በጉጉት እየጠበቅን ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀመረ አንቺ እቤት መጥተሽ እንደገና እንደ ቤተሰብ ስለምንኖር ነው፡፡ መምጣትሽን እንፈልገዋለን፤ ወላጆችሽ ነን፤ እንወድሻለን፤ በእጅጉ እንናፍቅሽማለን - ይህን ሃቅ በፍጹም አትርሺው! ለሁለት ቀናት ቢሆንም እንኳን ልታዪን ልትመጪ ግድ ይልሻል፤ ጊዜውን ለሌላ ለምንም ጉዳይ መስዋዕት እንዳታደርጊው፡፡ ነዪልን፤ አብሮነትሽን እንፈልገዋለን …
ደብዳቤውን አንብቤ ሳልጨርሰው ወደ ቤት ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ ከወላጆቼ ጋር ስድስት ቀናትን አሳልፌ ለፈተናዎቼ በሳምንቱ መጨረሻ ትምህርት ቤት ለመመለስ አቀድኩ፡፡ የጉዞ ዝግጅቴን ሳደርግ የሳራ ታናሽ ወንድም የሆነው ኦገስቲን ከእኔ ጋር ለበዓሉ ወደ ወላጆቼ ቤት ሄዶ መዋል ይችል እንደሆን ጠየቀኝ፡፡ ኦገስቲን የወንድሜ የቪያኒ የልብ ጓደኛ ሲሆን የመንፈቀ-ዓመቱን ትምህርቱን ኪጋሊ ላይ ካገባደደ በኋላ በትምህርት ቤት መኝታ ቤታችን ውስጥ ቆይቷል፡፡ መለሎው፣ መልከ-ቀናውና አስደሳቹ የ18 ዓመቱ ኦገስቲን ከቪያኒ በቀር ማንም ሰው ፊት አያወራም፡፡ እንግዳችን ቢሆንልን እንደምንደሰት ነገርኩት፡፡
ኦገስቲንና እኔ ማታባ ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ደረስን፤ የቤተሰቤም አባላት በመምጣቴ በእጅጉ ተደሰቱ፡፡ በሳይንስ የድህረ-ምረቃ ትምህርቱን ለመከታተል ዓለም አቀፍ የትምህርት ዕድል ካገኘው ከኤይማብል በስተቀር ቤተሰቡ ተሟልቷል፡፡ ኤይማብል አገሪቱን ለቆ ከ5 000 ኪሎሜትሮች በላይ ወደምትርቀው ሴኔጋል ሄዷል፡፡ ዳማሲን በበኩሉ በታሪክ በሁለተኛ ዲግሪ ከተመረቀ ጀምሮ ከሚያስተምርበት ከኪጋሊ ተሳፍሮ መጥቷል፡፡ ቪያኒም ከአዳሪ ትምህርት ቤት ተመልሷል፡፡
የመጀመሪያዋን ቀን ከዳማሲን የመንደር ወሬ ስሰማ፣ ጓደኞቼን ስጠይቅ፣ ከቪያኒ ጋር ስንጫወትና ስንከራከር አሳለፍኩ፡፡ በመጭው ቀን፣ በትንሳኤ እለት፣ አብረን ጥሩ ምግብ በላን፡፡ አምላክን ስለሰጠን ነገር ሁሉ አመስግነን በቤተሰባችንና በመንደራችን ስላለው ስለ ሁሉም ሰው ደህንነት ጸለይን - በተጨማሪም ስለብቸኛው ቀሪ አባላችን ስለ ኤይማብል ልዩ ጸሎት አደረስን፡፡ በላያችን ያንዣብብ ከነበረው የፖለቲካ ውጥረት በስተቀር አዝናኝ ጊዜ በማሳለፍ ላይ ነን፡፡ ከወላጆቼ ጋር በመሆኔ ደህንነትና ችግር-አልባነት ተሰማኝ - ይህም የሆነው ምንም ነገር ቢከሰት ታጽናናን ዘንድ እናቴ ስለምትኖርና አባቴም እኛን የመከላከሉን ሥራ ስለሚሠራ ነው፡፡ ቢያንስ ያንን ነው ያሰብኩት ፡፡
ይህ ምሽት የኛ ዓለም እስከዘላለሙ ልትቀየር ትንሽ የቀራት መሆኑን ለመገመት የሚያዳግትበት እንደወትሮው ያለ ምሽት መሆኑ ነው፡፡ ስለ ትምህርት፣ ሥራና በመንደሩ እየተከሰተ ስላለው ነገር እቤት ቁጭ ብለን እናወራለን፡፡ እናታችን ስለ ሠብሉ ስትነግረን አባታችን ደግሞ የቡና ኅብረት-ሥራው የትምህርት ወጪያቸውን ስለሚሸፍንላቸው ሕፃናት ያወራልናል፡፡ ኦገስቲንና ቪያኒ ይቃለዳሉ፡፡ እኔ በበኩሌ እየተዝናናሁና ሁሉንም ነገር እየታዘብኩ እቤት በመሆኔ ደስተኝነት ተሰምቶኛል፡፡ ያልተደሰተው ዳማሲን ብቻ ነው፡፡ ሁልጊዜ በዓል ላይ ሕይወት የሚዘራው እሱ የነበረ ቢሆንም ምሽቱን ሙሉ ሲብሰለሰልና በሥጋት ሲናጥ ቆይቷል፡፡
‹‹ዳማሲን ምን ሆነሃል?›› ስል ጠየኩት፡፡
ወንድሜ ቀና ሲል ዓይኖቻችን ተገጣጠሙ፡፡ ከዚያም በኋላ ዝም ብሎ መቆየት አልተቻለውም፡፡ በተጣደፈ ቃላትና ስሜት ሸክሙን እኔ ላይ አቃለለ - ‹‹ኢማኪዩሌ አይቻቸዋለሁ፤ ገዳዮቹን አይቻቸዋለሁ፡፡ ወደ ቦን ቤት ስንሄድ በርቀት አይተናቸዋል፡፡ የኢንተርሃምዌን ባለ ደማቅ ቀለማት ልብሶች ለብሰዋል፤ የእጅ ቦምቦችንም ይዘዋል፤
ቦምቦች ነበሯቸው ኢማኪዩሌ!›› ሲል ድምጹ አሰቀቀኝ፡፡
ሁሉም ሰው ንግግሩን ስለሰማው ቤቱ እርጭ አለ፡፡ ወላጆቼ እርስ በርሳቸው ተያዩና ዳማሲንን አዩት፡፡
አባቴ ልጁን ለማረጋጋት ሲል ‹‹ምናልባት ሐሳብህ አሸንፎህ እየወጣ እንዳይሆን›› አለው፡፡ ‹‹ብዙ መጥፎ ወሬ ይሰማል፡፡ ሰዎችም አደጋን በሌለበት እያዩት ነው፡፡››
‹‹አይ፣ ዝም ብዬ እኮ እየቃዠሁ አይደለም›› አለ ዳማሲን በድንገት ቆሞ የጉዳዩን አጣዳፊነት በሚያንጸባርቅ መልኩ በመናገር፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ሀገር_ቤት
፡
ሁልጊዜ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ የጥላቻ ድምፅ እሰማለሁ፡፡ የአር.ቲ. ኤል. ኤም. ሬድዮ የጥላቻ ድምጾች በመኝታ ቤቴ መስኮት ገብተው ህልሞቼ ውስጥ እስኪደነቀሩ ሌሊቱን በሰላም ተኝቼ አሳልፋለሁ፡፡ ልብ ይበሉ፣ በሦስተኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ አር. ቲ. ኤል. ኤም. በጽንፈኛ ሁቱዎች ዘንድ አዲሱና በጣም ታዋቂው ሬድዮ ጣቢያ ለመሆን ችሏል፡፡ ጸረ-ቱትሲ መርዝን የሚረጭ የተለየ የጥላቻ መሣሪያ ወጥቶታል፡፡
ሁሌ ‹‹ስለ ሁቱ የበላይነት›› የሚጮህ አካል-አልባ ክፉ ድምፅ ሆነ፡፡ የሁቱ የበላይነትም ሁቱዎችን በቱትሲ ወዳጆቻቸውና ጎረቤቶቻቸው ላይ እንዲነሱ የሚያደርግ ተናዳፊ ተርብ ለመሆን ቻለ፡፡ ‹‹እነዚያ በረሮ ቱትሲዎች ሊገድሉን ወጥተዋል፡፡ አትመኗቸው… እኛ ሁቱዎች ቀድመናቸው ልንነሳ ይገባናል! መንግሥታችንን ገልብጠው ሊያሳድዱን እየዶለቱብን ነው፡፡ በርዕሰ-ብሔራችን ላይ አንዳች ነገር ቢከሰት ሁሉንም ቱትሲዎች ወዲያውኑ ማውደም ግድ ይለናል! እያንዳንዱ ሁቱ ሩዋንዳን ከነዚህ ቱትሲ በረሮዎች ለማጽዳት እጅ ለእጅ መያያዝ
አለበት! የሁቱ የበላይነት! የሁቱ የበላይነት!››
ይህን በመሰለ አጉለኛ ሁኔታ ከእንቅልፌ እነቃለሁ፡፡ በእርግጥ ዘገባዎቹ እጅጉን በሚያስጠላ ሁኔታ እንጭጭ በመሆናቸው አልፎ አልፎ ያሥቃሉ፡፡ እነዚያን የልጅ ስድቦችና ልቅ ማስፈራሪያዎች ማንም ሰው ከምር ይቀበላቸዋል ብሎ ማመን አሰቸጋሪ ሲሆን መንግሥቱም የሕዝብ ንብረት የሆነውን የአየር ሰዓት ቱትሲዎችን ለማስፈራሪያ መፍቀዱን ማወቁ ይረብሻል፡፡ በወቅቱ ግን በሀገሪቱ በርካታ ስፍራዎች ቱትሲዎች በጽንፈኞች እየተገደሉ መሆኑን በሚገልጹ ወሬዎች ይበልጡን ተረበሽኩ፡፡ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እንዳሉት ጓደኞቼ ሁሉ በመገናኛ ብዙሃን ስለሚተላለፉት ዘገባዎች ብዙ ላለማሰብና ላለማውራት ሞከርኩ፡፡ ቤተሰቤ ሁሌ አስደሳችና ልዩ ጊዜ የሚያሳልፍበት የትንሣኤ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ ይህን የበዓል ወቅት ጎረቤቶቻችንን በመጋበዝና ወዳጅ-ዘመዶቻችንን በመጠየቅ እቤታችን እናሳልፋለን፡፡ የቤተሰቡ አባላት በሙሉ የምንገናኝበትን የትንሣኤን በዓል እቤቴ ማሳለፍ አምልጦኝ የማያውቅ ቢሆንም እየቀረቡ መጥተው ለነበሩት ፈተናዎቼ ለመዘጋጀት ያግዘኝ ዘንድ በትምህርት ቤቱ ለመቆየት ፈለግሁ፡፡ በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት ቆርጫለሁ፡፡ ወላጆቼ ስልክ ስላልነበራቸው ለአባቴ ለምን እቤት እንደማልሄድ የሚያብራራ ደብዳቤ ጻፍኩለት፡፡ ወላጆቼ ሁልጊዜ ልጆቻቸው የተሻለ ውጤት ያመጡ ዘንድ
ከሚጠበቀው በላይ እንዲያጠኑ ስለሚፈልጉ ቅር እንደማይሰኙብኝ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይህ ለካ ትልቅ ስህተት ኖሯል!
አባቴ እቤት እንድሄድ የሚለምን ደብዳቤ ጻፈልኝ፡፡ እንዲያውም የጠየቀኝ የትምህርት ቤት እረፍቴ እስኪደርስ ሳልጠብቅ ወዲያውኑ እንድሄድ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንድሆን እንደሚፈልግና እቤት ያላንዳች ረብሻ ማጥናት እንደሚቻለኝ ቃል ገባልኝ፡፡ ልባዊ ተማጽኖው በዓይኖቼ እንባ ሞላባቸው፡፡ ውድ ልጄ፣
ትምህርት አንቺን ከኛ እንደነጠቀን ይሰማኛል፡፡ እናትሽና እኔ እረፍትሽ እስኪጀምር በጉጉት እየጠበቅን ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀመረ አንቺ እቤት መጥተሽ እንደገና እንደ ቤተሰብ ስለምንኖር ነው፡፡ መምጣትሽን እንፈልገዋለን፤ ወላጆችሽ ነን፤ እንወድሻለን፤ በእጅጉ እንናፍቅሽማለን - ይህን ሃቅ በፍጹም አትርሺው! ለሁለት ቀናት ቢሆንም እንኳን ልታዪን ልትመጪ ግድ ይልሻል፤ ጊዜውን ለሌላ ለምንም ጉዳይ መስዋዕት እንዳታደርጊው፡፡ ነዪልን፤ አብሮነትሽን እንፈልገዋለን …
ደብዳቤውን አንብቤ ሳልጨርሰው ወደ ቤት ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ ከወላጆቼ ጋር ስድስት ቀናትን አሳልፌ ለፈተናዎቼ በሳምንቱ መጨረሻ ትምህርት ቤት ለመመለስ አቀድኩ፡፡ የጉዞ ዝግጅቴን ሳደርግ የሳራ ታናሽ ወንድም የሆነው ኦገስቲን ከእኔ ጋር ለበዓሉ ወደ ወላጆቼ ቤት ሄዶ መዋል ይችል እንደሆን ጠየቀኝ፡፡ ኦገስቲን የወንድሜ የቪያኒ የልብ ጓደኛ ሲሆን የመንፈቀ-ዓመቱን ትምህርቱን ኪጋሊ ላይ ካገባደደ በኋላ በትምህርት ቤት መኝታ ቤታችን ውስጥ ቆይቷል፡፡ መለሎው፣ መልከ-ቀናውና አስደሳቹ የ18 ዓመቱ ኦገስቲን ከቪያኒ በቀር ማንም ሰው ፊት አያወራም፡፡ እንግዳችን ቢሆንልን እንደምንደሰት ነገርኩት፡፡
ኦገስቲንና እኔ ማታባ ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ደረስን፤ የቤተሰቤም አባላት በመምጣቴ በእጅጉ ተደሰቱ፡፡ በሳይንስ የድህረ-ምረቃ ትምህርቱን ለመከታተል ዓለም አቀፍ የትምህርት ዕድል ካገኘው ከኤይማብል በስተቀር ቤተሰቡ ተሟልቷል፡፡ ኤይማብል አገሪቱን ለቆ ከ5 000 ኪሎሜትሮች በላይ ወደምትርቀው ሴኔጋል ሄዷል፡፡ ዳማሲን በበኩሉ በታሪክ በሁለተኛ ዲግሪ ከተመረቀ ጀምሮ ከሚያስተምርበት ከኪጋሊ ተሳፍሮ መጥቷል፡፡ ቪያኒም ከአዳሪ ትምህርት ቤት ተመልሷል፡፡
የመጀመሪያዋን ቀን ከዳማሲን የመንደር ወሬ ስሰማ፣ ጓደኞቼን ስጠይቅ፣ ከቪያኒ ጋር ስንጫወትና ስንከራከር አሳለፍኩ፡፡ በመጭው ቀን፣ በትንሳኤ እለት፣ አብረን ጥሩ ምግብ በላን፡፡ አምላክን ስለሰጠን ነገር ሁሉ አመስግነን በቤተሰባችንና በመንደራችን ስላለው ስለ ሁሉም ሰው ደህንነት ጸለይን - በተጨማሪም ስለብቸኛው ቀሪ አባላችን ስለ ኤይማብል ልዩ ጸሎት አደረስን፡፡ በላያችን ያንዣብብ ከነበረው የፖለቲካ ውጥረት በስተቀር አዝናኝ ጊዜ በማሳለፍ ላይ ነን፡፡ ከወላጆቼ ጋር በመሆኔ ደህንነትና ችግር-አልባነት ተሰማኝ - ይህም የሆነው ምንም ነገር ቢከሰት ታጽናናን ዘንድ እናቴ ስለምትኖርና አባቴም እኛን የመከላከሉን ሥራ ስለሚሠራ ነው፡፡ ቢያንስ ያንን ነው ያሰብኩት ፡፡
ይህ ምሽት የኛ ዓለም እስከዘላለሙ ልትቀየር ትንሽ የቀራት መሆኑን ለመገመት የሚያዳግትበት እንደወትሮው ያለ ምሽት መሆኑ ነው፡፡ ስለ ትምህርት፣ ሥራና በመንደሩ እየተከሰተ ስላለው ነገር እቤት ቁጭ ብለን እናወራለን፡፡ እናታችን ስለ ሠብሉ ስትነግረን አባታችን ደግሞ የቡና ኅብረት-ሥራው የትምህርት ወጪያቸውን ስለሚሸፍንላቸው ሕፃናት ያወራልናል፡፡ ኦገስቲንና ቪያኒ ይቃለዳሉ፡፡ እኔ በበኩሌ እየተዝናናሁና ሁሉንም ነገር እየታዘብኩ እቤት በመሆኔ ደስተኝነት ተሰምቶኛል፡፡ ያልተደሰተው ዳማሲን ብቻ ነው፡፡ ሁልጊዜ በዓል ላይ ሕይወት የሚዘራው እሱ የነበረ ቢሆንም ምሽቱን ሙሉ ሲብሰለሰልና በሥጋት ሲናጥ ቆይቷል፡፡
‹‹ዳማሲን ምን ሆነሃል?›› ስል ጠየኩት፡፡
ወንድሜ ቀና ሲል ዓይኖቻችን ተገጣጠሙ፡፡ ከዚያም በኋላ ዝም ብሎ መቆየት አልተቻለውም፡፡ በተጣደፈ ቃላትና ስሜት ሸክሙን እኔ ላይ አቃለለ - ‹‹ኢማኪዩሌ አይቻቸዋለሁ፤ ገዳዮቹን አይቻቸዋለሁ፡፡ ወደ ቦን ቤት ስንሄድ በርቀት አይተናቸዋል፡፡ የኢንተርሃምዌን ባለ ደማቅ ቀለማት ልብሶች ለብሰዋል፤ የእጅ ቦምቦችንም ይዘዋል፤
ቦምቦች ነበሯቸው ኢማኪዩሌ!›› ሲል ድምጹ አሰቀቀኝ፡፡
ሁሉም ሰው ንግግሩን ስለሰማው ቤቱ እርጭ አለ፡፡ ወላጆቼ እርስ በርሳቸው ተያዩና ዳማሲንን አዩት፡፡
አባቴ ልጁን ለማረጋጋት ሲል ‹‹ምናልባት ሐሳብህ አሸንፎህ እየወጣ እንዳይሆን›› አለው፡፡ ‹‹ብዙ መጥፎ ወሬ ይሰማል፡፡ ሰዎችም አደጋን በሌለበት እያዩት ነው፡፡››
‹‹አይ፣ ዝም ብዬ እኮ እየቃዠሁ አይደለም›› አለ ዳማሲን በድንገት ቆሞ የጉዳዩን አጣዳፊነት በሚያንጸባርቅ መልኩ በመናገር፡
👍2😁1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_ስድስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#መመለስ_አይታሰብም
፡
እናቴ፣ አባቴ፣ ዳማሲን፣ ቪያኒ፣ ኦገስቲንና እኔ ቀኑን ሙሉ በግቢያችን ውስጥ በፍርሃት ተቆራምደን ሬድዮ ስናዳምጥ ዋልን፡፡ ከሀገራችን ውጪ የሚተላለፉት ዘገባዎች ተራ ሁቱ ዜጎች የመንግሥቱን ሰራዊትና የኢንተርሃምዌ ታጣቂዎችን ያልታጠቁ ንጹሃን ቱትሲዎችን በመግደሉ ተግባር ላይ እየተቀላቀሏቸው እንደሚገኙ ዘገቡ፡፡ የሀገር ውስጥ ጣቢያዎች በበኩላቸው ሁቱዎች ገጀራ እያነሱ ቱትሲ ጎረቤቶቻቸውን እንዲያጠቁ ያበረታቱ ገቡ፡፡
እንደ ትንሽ ልጅ አደረገኝ - ወላጆቼ ምን እንደማደርግ እንዲመሩኝ ተመኘሁ፡፡ ከ1959 ጀምሮ ከፖለቲካ አለመረጋጋቶችና ከቱትሲ ጭፍጨፋዎች ስለተረፉ መቼም ምን ማድረግ እንዳለባቸው ማወቃቸው አይቀርም ስል አሰብኩ፡፡ ብሔራዊው ሬድዮ ጣቢያ ሕዝቡ በየቤቱ እንዲቆይ አስጠነቀቀ፤ እኛም የወላጆቻቸውን ምክር እንደሚሰሙ ማለፊያ ልጆች ተቀበልነው፡፡ ከአጥራችን ውጪ ምን እየተከሰተ እንደነበር ለማወቅ በራችንን ለመክፈት እንኳን በጣም ፈራን፡፡ ከቅጥር-ግቢያችን ውጪ መንቀሳቀስ አደጋ ይኖረዋል ወይንም ሞት ያስከትላል ብለን እንደ እስረኛ እንቅስቃሴያችንን በቤት ውስጥ ገደብን፡፡
ስልክ አልነበረንም፤ ቢኖርም ኖሮ እንኳን አብዛኞቹ የሀገሪቱ የስልክ መስመሮች ዝግ ናቸው፡፡ ሬድዮናችን ከሚያደርሰን ወሬ በቀር ከማንም ጋር ግንኙነት የምናደርግበት መንገድ አልነበረም፡፡ ራሴን ልስት መሆኑ አስኪሰማኝ ድረስ ስለ አሰቃቂዎቹ ግድያዎች ስንሰማ ለሰዓታት ተቀመጥን፡፡ ጥላ በረድ ሲል መጻሕፍቴን ሳብ አድርጌ ለፈተናዎቼ መዘጋጀት ጀመርኩ፡፡
‹‹እንዴት ይሆንልሻል ኢማኪዩሌ?›› ሲል ዳማሲን ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ለማጥናት የሚሆንሽን ጽናትስ ከየት አመጣሽው? ተመልሰሽ ትምህርት ቤት እንደምትገቢስ ለምን ታስቢያለሽ?››
ወንድሜ ከሰዓታት በፊት ተስፋ ስቆርጥ ሲያጽናናኝ እንዳልነበር አሁን ራሱም ተስፋ ቆረጠ፡፡ ለመበርታት ተራው የኔ ስለሆነ ‹‹መጨነቅህን ተው›› አልኩት፡፡ ‹‹ይህን እናልፈዋለን፤ ሁኔታዎች ከተባባሱ በድንበሩ በኩል እንሾልካለን፡፡ እማማና አባባ ካሁን በፊት ይህን ዓይነቱን ችግር አልፈውታል፡፡ እምነት ይኑርህ፡፡››
ስለ እውነት ለመናገር ግን እኔ ራሴ ያለኝ እምነት ተሟጧል - የማጠናው ከቤተሰቤ ጭንቀት ላይ ሐሳቤን ለማንሳት አስቤ እንጂ ለፈተና ለመዘጋጀት አልነበረም፡፡
በእለቱ የሰማነው ብቸኛው አበረታች ዜና መነሻቸውን በዩጋንዳ ያደረጉት የቱትሲ አማጽያኑን መሪ የሩአጉን የፖል ካጋሜን መልዕክት ነው፡፡ በቱትሲዎች ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎች ካላቆሙ በስተቀረ እየተፋለሙ ሩዋንዳን ለመውረርና ቱትሲዎችን ለመታደግ እስከመጨረሻው እንደሚጸኑ ቃል ገቡ፡፡ ካጋሜ ያንን ሲሉ መስማቱ ያበረታታል፤ ሆኖም ግን ብቸኛው ‹‹መልካም›› ዜና የለየለት ጦርነት እንከፍታለን የሚል ማስፈራሪያ ብቻ በመሆኑ አዘንኩ፡፡ በዚያ ምሽት ማናችንም ከጥቂት ደቂቃዎች በላይ አልተኛንም፡፡ በሚቀጥለው ቀን በኪጋሊ ከሚኖሩት ከለዘብተኛ ሁቱዋ የሩዋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ከአጋቴ ጋር የተደረገ የቢቢሲን የስልክ ቃለ-መጠይቅ ሰማን፡፡ ምንም እንኳን የተ.መ.ድ ሰላም አስከባሪዎች እየጠበቋቸው ቢሆንም በቤታቸው ዙሪያ ሁሉ የጥይት እሩምታ ይሰማል፡፡ በዚህ ንግግራቸው ወቅት እርሳቸው፣ ባለቤታቸውና አምስት ልጆቻቸው ወለል ላይ መተኛታቸውንና የማምለጫ መንገድም እንደሌላቸው ገለጹ፡፡ ወዲውኑም ቃለ-መጠይቁ ሳያልቅ የስልክ መስመሩ ተቋረጠ፡፡ በኋላ እንደሰማነው ወታደሮች ወደ ቤታቸው ድንገት ገብተው እርሳቸውንና ባለቤታቸውን ገድለዋቸዋል፡፡ ትረፉ ሲላቸው ልጆቻቸው አልተገደሉም፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሯ ቃላት ስሜታችንን በእጅጉ ነኩት፤ በዚህ ወቅት ሁኔታዎች ይሻሻላሉ ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ ገዳዮቹ ሁቱዋን ጠቅላይ ሚኒስትር ከገደሉ እኛንስ ከመግደል ምን ያቆማቸዋል?
በነዚያ 24 ሰዓታት የነበረው ረፍት-አልባ ውጥረት ቤተሰቤን ጎዳው፡፡ እናቴ በደመ-ነፍስ ከክፍል ክፍል እየተዘዋወረች የነበረንን ማንኛውንም ሻንጣ እጇ በገቡላት እቃዎች ትሞላለች፡፡ ‹‹በስንት ልፋት ያሟላኋቸውን እቃዎች ሰዎች እንዲዘርፏቸው ትቼ አልሄድም›› አለችን፡፡ ‹‹አርቄ እደብቃቸዋለሁ፡፡ እንድ ቀን ተመልሰን እናገኛቸዋለን፡፡››
ወዴት ለመሄድ እንዳቀደች አላወቅሁም፡፡ ብቸኛው ሊያስኬደን የሚችለው የማምለጫው መንገዳችን (የኪቩ ሐይቅን አቋርጦ) በኢንተርሃምዌ ታጣቂዎች እንደተዘጋ ሰምተናል፡፡ ወደ ሐይቁ የሚጠጋን ማናቸውንም ቱትሲም ሆነ ለዘብተኛ ሁቱ በመግደል ላይ ናቸው፡፡
አባቴ በግራ መጋባት ነባራዊውን ሁኔታ ሊያምን አልቻለም፡፡ ‹‹ግድያው ከቀጠለ ሩአግ ሊያቆመው ጣልቃ ይገባል፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ እዚህ ይመጡና ያድኑናል›› ሲል ግምቱን ይነግረን ጀመር፡፡
ለማመን ተቸግሬ ‹‹አባባ ምን እያሰብክ ነው›› ስል ጠየኩት፡፡ ‹‹የሩአግ ወታደሮች ገና በስተሰሜን በዩጋንዳ ድንበር አቅራቢያ ናቸው፡፡ ተሽከርካሪ ስለሌላቸው በእግራቸው እየተጓዙ ጦሩንና ኢተርሃምዌን መዋጋት ግድ ይላቸዋል፡፡ እዚህ ለመድረስ ሳምንታት ይፈጅባቸዋል … ከነጭራሹ እዚህ መድረስ መቻላቸውንስ ማን ያውቃል!››
ከአባቴ ጋር የተከራከርኩባቸውን ውሱን ጊዜያት መጥቀስ እችላለሁ፤ ያለወትሮዬ መሟገቴ ሁሉም ነገር በመቀያየር ላይ በመሆኑ ነው፡፡ ወላጆቼ በትክክል እያሰቡ አይደለም፤ ኦገስቲንና ቪያኒም ልጆች ስለሆኑና ስለተደናገጡ ሊታመንባቸው አይችልም፡፡ በሕይወቴ ሙሉ የዳማሲንን መርህ እከተላለሁ፤ አሁን ግን ወደ ክፍሉ አፈግፍጎ ግድግዳ ላይ አፍጥጧል፡፡
ፈልጌው ወደ ክፍሉ እንደገባሁ ‹‹እስኪ እንዲያው የምታስቢውን ሳትደብቂ ንገሪኝ፤ ይችን ቀን የምናልፋት ይመስልሻል?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ይኸውልሽ በመጪው ዓመት የማደርገውን ነገር ተኝቼ ለማለም እየሞከርኩ ነው፤ ግን አልሆነልኝም፡፡ በሕይወት የምኖር አይመስለኝም፡፡ የወደፊት ሕይወት የለኝም፡፡››
‹‹ዳማሲን ከዚህ ነገር ውስጥ እንደምንም መውጣት አለብህ!›› ስል ጮህኩበት፡፡‹‹ትግሉን ገና ሳትጀምር ተስፋ መቁረጥ የለብህም!›› አንተ በመጭው ዓመት ምን እንደምትሠራ ማየት ካልቻልክ እኔ እችላለሁ! ከዩኒቨርሲቲ ስመረቅ ቡታሬ እኔ ጋ ትመጣለህ፡፡ ዲፕሎማዬን ስቀበል በፊት ወንበር ተቀምጠህ እያጨበጨብክ በደስታ ትጮሃለህ፡፡ ስለዚህ አሁን ተነሥና እነእማማን አግዛቸው!››
‹‹ምናለ ያንቺ እምነትና ጽናት ቢኖረኝ›› ብሎ ተነፈሰና መልሶ ግድግዳውን አተኩሮ ያይ ገባ፡፡
እኔ ብርታቱ ባይኖረኝም አንድ ሰው መልሶ ቤተሰቤን ማረጋጋት አለበት፡፡ ቤተሰቡ በለየለት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ እንዳይገባ ለመበርታትና ቢያንስ ጠንክሬ ለመሥራት ሞከርኩ፡፡
ለጠቅላይ ሚኒስትሯ ጥበቃ ያደርጉ የነበሩ አሥር ቤልጅየማውያን የተመድ ሰላም አስካባሪዎች በመንግሥት ወታደሮች እንደተገደሉና በሩዋንዳ የሚኖሩ የቤልጅዬም ዜጎች ሁሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ምሽት ላይ ሰማን፡፡ ቤልጅዬማውያኑና የሌሎች ሀገር ዜጎች አገሪቱን ለቀው ከወጡ ይህን የለየለትን ጭፍጨፋ ለማስቆም ዐቅሙ ያለው ሌላ ማንም ሊኖር እንደማይችል እናውቃለን፡፡ በዚህ ምሽትም ስላልተኛን ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሁላችንም እንቅልፍ አጣን ማለት ነው፡፡
ንጋት ላይ ጩኸት ይሰማን ጀመር፡፡
፡
፡
#ምዕራፍ_ስድስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#መመለስ_አይታሰብም
፡
እናቴ፣ አባቴ፣ ዳማሲን፣ ቪያኒ፣ ኦገስቲንና እኔ ቀኑን ሙሉ በግቢያችን ውስጥ በፍርሃት ተቆራምደን ሬድዮ ስናዳምጥ ዋልን፡፡ ከሀገራችን ውጪ የሚተላለፉት ዘገባዎች ተራ ሁቱ ዜጎች የመንግሥቱን ሰራዊትና የኢንተርሃምዌ ታጣቂዎችን ያልታጠቁ ንጹሃን ቱትሲዎችን በመግደሉ ተግባር ላይ እየተቀላቀሏቸው እንደሚገኙ ዘገቡ፡፡ የሀገር ውስጥ ጣቢያዎች በበኩላቸው ሁቱዎች ገጀራ እያነሱ ቱትሲ ጎረቤቶቻቸውን እንዲያጠቁ ያበረታቱ ገቡ፡፡
እንደ ትንሽ ልጅ አደረገኝ - ወላጆቼ ምን እንደማደርግ እንዲመሩኝ ተመኘሁ፡፡ ከ1959 ጀምሮ ከፖለቲካ አለመረጋጋቶችና ከቱትሲ ጭፍጨፋዎች ስለተረፉ መቼም ምን ማድረግ እንዳለባቸው ማወቃቸው አይቀርም ስል አሰብኩ፡፡ ብሔራዊው ሬድዮ ጣቢያ ሕዝቡ በየቤቱ እንዲቆይ አስጠነቀቀ፤ እኛም የወላጆቻቸውን ምክር እንደሚሰሙ ማለፊያ ልጆች ተቀበልነው፡፡ ከአጥራችን ውጪ ምን እየተከሰተ እንደነበር ለማወቅ በራችንን ለመክፈት እንኳን በጣም ፈራን፡፡ ከቅጥር-ግቢያችን ውጪ መንቀሳቀስ አደጋ ይኖረዋል ወይንም ሞት ያስከትላል ብለን እንደ እስረኛ እንቅስቃሴያችንን በቤት ውስጥ ገደብን፡፡
ስልክ አልነበረንም፤ ቢኖርም ኖሮ እንኳን አብዛኞቹ የሀገሪቱ የስልክ መስመሮች ዝግ ናቸው፡፡ ሬድዮናችን ከሚያደርሰን ወሬ በቀር ከማንም ጋር ግንኙነት የምናደርግበት መንገድ አልነበረም፡፡ ራሴን ልስት መሆኑ አስኪሰማኝ ድረስ ስለ አሰቃቂዎቹ ግድያዎች ስንሰማ ለሰዓታት ተቀመጥን፡፡ ጥላ በረድ ሲል መጻሕፍቴን ሳብ አድርጌ ለፈተናዎቼ መዘጋጀት ጀመርኩ፡፡
‹‹እንዴት ይሆንልሻል ኢማኪዩሌ?›› ሲል ዳማሲን ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ለማጥናት የሚሆንሽን ጽናትስ ከየት አመጣሽው? ተመልሰሽ ትምህርት ቤት እንደምትገቢስ ለምን ታስቢያለሽ?››
ወንድሜ ከሰዓታት በፊት ተስፋ ስቆርጥ ሲያጽናናኝ እንዳልነበር አሁን ራሱም ተስፋ ቆረጠ፡፡ ለመበርታት ተራው የኔ ስለሆነ ‹‹መጨነቅህን ተው›› አልኩት፡፡ ‹‹ይህን እናልፈዋለን፤ ሁኔታዎች ከተባባሱ በድንበሩ በኩል እንሾልካለን፡፡ እማማና አባባ ካሁን በፊት ይህን ዓይነቱን ችግር አልፈውታል፡፡ እምነት ይኑርህ፡፡››
ስለ እውነት ለመናገር ግን እኔ ራሴ ያለኝ እምነት ተሟጧል - የማጠናው ከቤተሰቤ ጭንቀት ላይ ሐሳቤን ለማንሳት አስቤ እንጂ ለፈተና ለመዘጋጀት አልነበረም፡፡
በእለቱ የሰማነው ብቸኛው አበረታች ዜና መነሻቸውን በዩጋንዳ ያደረጉት የቱትሲ አማጽያኑን መሪ የሩአጉን የፖል ካጋሜን መልዕክት ነው፡፡ በቱትሲዎች ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎች ካላቆሙ በስተቀረ እየተፋለሙ ሩዋንዳን ለመውረርና ቱትሲዎችን ለመታደግ እስከመጨረሻው እንደሚጸኑ ቃል ገቡ፡፡ ካጋሜ ያንን ሲሉ መስማቱ ያበረታታል፤ ሆኖም ግን ብቸኛው ‹‹መልካም›› ዜና የለየለት ጦርነት እንከፍታለን የሚል ማስፈራሪያ ብቻ በመሆኑ አዘንኩ፡፡ በዚያ ምሽት ማናችንም ከጥቂት ደቂቃዎች በላይ አልተኛንም፡፡ በሚቀጥለው ቀን በኪጋሊ ከሚኖሩት ከለዘብተኛ ሁቱዋ የሩዋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ከአጋቴ ጋር የተደረገ የቢቢሲን የስልክ ቃለ-መጠይቅ ሰማን፡፡ ምንም እንኳን የተ.መ.ድ ሰላም አስከባሪዎች እየጠበቋቸው ቢሆንም በቤታቸው ዙሪያ ሁሉ የጥይት እሩምታ ይሰማል፡፡ በዚህ ንግግራቸው ወቅት እርሳቸው፣ ባለቤታቸውና አምስት ልጆቻቸው ወለል ላይ መተኛታቸውንና የማምለጫ መንገድም እንደሌላቸው ገለጹ፡፡ ወዲውኑም ቃለ-መጠይቁ ሳያልቅ የስልክ መስመሩ ተቋረጠ፡፡ በኋላ እንደሰማነው ወታደሮች ወደ ቤታቸው ድንገት ገብተው እርሳቸውንና ባለቤታቸውን ገድለዋቸዋል፡፡ ትረፉ ሲላቸው ልጆቻቸው አልተገደሉም፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሯ ቃላት ስሜታችንን በእጅጉ ነኩት፤ በዚህ ወቅት ሁኔታዎች ይሻሻላሉ ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ ገዳዮቹ ሁቱዋን ጠቅላይ ሚኒስትር ከገደሉ እኛንስ ከመግደል ምን ያቆማቸዋል?
በነዚያ 24 ሰዓታት የነበረው ረፍት-አልባ ውጥረት ቤተሰቤን ጎዳው፡፡ እናቴ በደመ-ነፍስ ከክፍል ክፍል እየተዘዋወረች የነበረንን ማንኛውንም ሻንጣ እጇ በገቡላት እቃዎች ትሞላለች፡፡ ‹‹በስንት ልፋት ያሟላኋቸውን እቃዎች ሰዎች እንዲዘርፏቸው ትቼ አልሄድም›› አለችን፡፡ ‹‹አርቄ እደብቃቸዋለሁ፡፡ እንድ ቀን ተመልሰን እናገኛቸዋለን፡፡››
ወዴት ለመሄድ እንዳቀደች አላወቅሁም፡፡ ብቸኛው ሊያስኬደን የሚችለው የማምለጫው መንገዳችን (የኪቩ ሐይቅን አቋርጦ) በኢንተርሃምዌ ታጣቂዎች እንደተዘጋ ሰምተናል፡፡ ወደ ሐይቁ የሚጠጋን ማናቸውንም ቱትሲም ሆነ ለዘብተኛ ሁቱ በመግደል ላይ ናቸው፡፡
አባቴ በግራ መጋባት ነባራዊውን ሁኔታ ሊያምን አልቻለም፡፡ ‹‹ግድያው ከቀጠለ ሩአግ ሊያቆመው ጣልቃ ይገባል፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ እዚህ ይመጡና ያድኑናል›› ሲል ግምቱን ይነግረን ጀመር፡፡
ለማመን ተቸግሬ ‹‹አባባ ምን እያሰብክ ነው›› ስል ጠየኩት፡፡ ‹‹የሩአግ ወታደሮች ገና በስተሰሜን በዩጋንዳ ድንበር አቅራቢያ ናቸው፡፡ ተሽከርካሪ ስለሌላቸው በእግራቸው እየተጓዙ ጦሩንና ኢተርሃምዌን መዋጋት ግድ ይላቸዋል፡፡ እዚህ ለመድረስ ሳምንታት ይፈጅባቸዋል … ከነጭራሹ እዚህ መድረስ መቻላቸውንስ ማን ያውቃል!››
ከአባቴ ጋር የተከራከርኩባቸውን ውሱን ጊዜያት መጥቀስ እችላለሁ፤ ያለወትሮዬ መሟገቴ ሁሉም ነገር በመቀያየር ላይ በመሆኑ ነው፡፡ ወላጆቼ በትክክል እያሰቡ አይደለም፤ ኦገስቲንና ቪያኒም ልጆች ስለሆኑና ስለተደናገጡ ሊታመንባቸው አይችልም፡፡ በሕይወቴ ሙሉ የዳማሲንን መርህ እከተላለሁ፤ አሁን ግን ወደ ክፍሉ አፈግፍጎ ግድግዳ ላይ አፍጥጧል፡፡
ፈልጌው ወደ ክፍሉ እንደገባሁ ‹‹እስኪ እንዲያው የምታስቢውን ሳትደብቂ ንገሪኝ፤ ይችን ቀን የምናልፋት ይመስልሻል?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ‹‹ይኸውልሽ በመጪው ዓመት የማደርገውን ነገር ተኝቼ ለማለም እየሞከርኩ ነው፤ ግን አልሆነልኝም፡፡ በሕይወት የምኖር አይመስለኝም፡፡ የወደፊት ሕይወት የለኝም፡፡››
‹‹ዳማሲን ከዚህ ነገር ውስጥ እንደምንም መውጣት አለብህ!›› ስል ጮህኩበት፡፡‹‹ትግሉን ገና ሳትጀምር ተስፋ መቁረጥ የለብህም!›› አንተ በመጭው ዓመት ምን እንደምትሠራ ማየት ካልቻልክ እኔ እችላለሁ! ከዩኒቨርሲቲ ስመረቅ ቡታሬ እኔ ጋ ትመጣለህ፡፡ ዲፕሎማዬን ስቀበል በፊት ወንበር ተቀምጠህ እያጨበጨብክ በደስታ ትጮሃለህ፡፡ ስለዚህ አሁን ተነሥና እነእማማን አግዛቸው!››
‹‹ምናለ ያንቺ እምነትና ጽናት ቢኖረኝ›› ብሎ ተነፈሰና መልሶ ግድግዳውን አተኩሮ ያይ ገባ፡፡
እኔ ብርታቱ ባይኖረኝም አንድ ሰው መልሶ ቤተሰቤን ማረጋጋት አለበት፡፡ ቤተሰቡ በለየለት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ እንዳይገባ ለመበርታትና ቢያንስ ጠንክሬ ለመሥራት ሞከርኩ፡፡
ለጠቅላይ ሚኒስትሯ ጥበቃ ያደርጉ የነበሩ አሥር ቤልጅየማውያን የተመድ ሰላም አስካባሪዎች በመንግሥት ወታደሮች እንደተገደሉና በሩዋንዳ የሚኖሩ የቤልጅዬም ዜጎች ሁሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ምሽት ላይ ሰማን፡፡ ቤልጅዬማውያኑና የሌሎች ሀገር ዜጎች አገሪቱን ለቀው ከወጡ ይህን የለየለትን ጭፍጨፋ ለማስቆም ዐቅሙ ያለው ሌላ ማንም ሊኖር እንደማይችል እናውቃለን፡፡ በዚህ ምሽትም ስላልተኛን ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሁላችንም እንቅልፍ አጣን ማለት ነው፡፡
ንጋት ላይ ጩኸት ይሰማን ጀመር፡፡
👍1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ልጆቹን_ስሰናበት
፡
ዳማሲን ከመሄዱ የቄሱ ግቢ የፊት በር ተንኳኳ፡፡ ያንኳኳው የቪያኒ የሁለተኛ ደረጃ መምህር የሆነው ንዚማ ሲሆን አመጣጡም ቄስ ሙሪንዚን ፈልጎ ነው፡፡ የሹክሹክታ ንግግር ከተደረገ በኋላ በሩ ተዘጋ፡፡ ወጥቼ ንዚማን በቄሱ ዛፍ ጥላ ስር ተቀምጦ አገኘሁት፡፡ በዚያ ደብዘዝ ባለው ብርሃንም ቢሆን በፊቱ ላይ የሚነበበውን ህመም ማየት አይከብድም፡፡
እንደፈራ ልጅ አድርጎታል - ‹‹ምን ያደርጉናል? የሚገድሉን ይመስልሻል?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡
በሩ ጋ መምጣቱን እንደሰማሁ በራስ ወዳድነት ስሜት ተውጬ የማበረታቻ ቃላት ይሰነዝርልኝና ጥንካሬ ይለግሰኝ ዘንድ ተመኝቻለሁ፤ ግን እርሱ ነው ሁለቱንም ላያገኛቸው ይሻቸው የያዘው፡፡
መምህር ንዚማ ሚስትና ልጆቹ ራቅ ባለ መንደር አማቱን ሊጠይቁ ሄደዋል፡፡ ደኅና ስለመሆናቸው ምንም የሚያውቅበት መንገድ ስላጣና ጥርጣሬ ስለገባው ተሰቃየ፡፡ ‹‹የማልተዋቸው ህልሞች አሉኝ›› አለ፡፡ ‹‹ሚስቴና ልጆቼ ሲታረዱና እፊቴ ሲቆራረጡ ይታየኛል፡፡ ይህን ለማስቆም እንደምታዪኝ ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ በአሁኑ ሰዓት እኮ ተገድለው መንገድ ላይ ተጥለው ነው የሚሆነው፡፡›› በቻልኩት መጠን ላጽናናው ሞከርኩ፤ ግን ምን ልለው እችላለሁ? እኔ ራሴ እርግጠኛ ባልሆንኩበት ሁኔታ ነገሮች ጥሩ ሊሆኑ እንደሚችሉ ስንት ጊዜ ልናገር?
በጣም አቃሰተና ‹‹የት አባቴ ልግባ? ውጪ ያለው ሁሉም ሰው ገጀራ ይዟል፤ ጠመንጃ የያዙም አይቻለሁ፡፡››
‹‹ግድያው እስኪያቆም ድረስ እዚህ ቆያ፤ ከዚያም ከቤተሰብህ ትገናኛለህ›› አልኩት መንፈሱን ለማረጋጋት፡፡
ራሱን ነቅንቆ ቆመና ‹‹ልጄ፣ እዚህ አልቆይም፤ ሌላ የምሄድበት ቦታም የለኝ፡፡››
‹‹እጸልይልሃለሁ፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ ኢማኪዩሌ፡፡››
ተሰናብቶኝ ቄስ ሙሪንዚ ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ቤቱ ፊት ለፊት ሄደ፡፡ ቄሱ ንዚማን እንደማይሸሽጉት ነግረውት ሳይሆን አይቀርም በሩን በእጃቸው ሲያመላክቱት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ወጣ፡፡ በኋላ እንደሰማሁት ይህ ምስኪን ሰው ተቆራርጦ የተገደለው ከቄሱ ቤት ጥቂት መቶ ሜትሮች ርቆ ባለ መንገድ ላይ ነው፡፡ ከተወሰኑ ሰዓታት በኋላ ብቻዬን በተቀመጥኩባት በአንዲት ትንሽ መኝታ ክፍል ቄስ ሙሪንዚ ሌሎች አምስት ቱትሲ ሴቶችን በጸጥታ አስገቡ፡፡ ሁሉም የአካባቢያችን ሰዎች እንደሆኑ ባውቅም አንዳቸውንም በደንብ አላወቅኋቸውም፡፡ ሴቶቹን ወደ ክፍሏ ሲያመጧቸው ቄሱ ተደናግጠዋል፡፡ ‹‹ፍጠኑ፣ ፍጠኑ!›› የሚንሾካሾኩት በጣም በፍጥነት ስለሆነ ልንሰማቸው አልቻልንም፡፡ ‹‹እዚህ ጠብቁኝ፤ ታዲያ ደሞ ዝም በሉ እሺ›› አሉን በሩን ዘግተው ሲወጡ፡፡ አብረን የነበርነው ስድስት ቱትሲ ሴቶች ከሞላ ጎደል እርስ በርስ የማንተዋወቅ ቢሆንም ሁለት ነገሮች ግን ያመሳስሉናል - እየታደንን መሆናችንና የምንደበቅበት ምንም ስፍራ የሌለን መሆኑ፡፡ ለመናገርም ሆነ ለመተዋወቅ በጣም ፈርተን እርስ በርሳችን እየተያየን ቆመናል፡፡ ውጪ ምን እየተከሰተ እንዳለ አናውቅም፣ ከቄሱ ድንጋጤ እንደተረዳነው ግን ነገሮች ተበለሻሽተዋል፡፡
ከቤቱ ውጪ ድንገት ጩኸቶች ይሰሙ ጀመር - በእጆቻችን ላይ ያሉትን ጸጉሮች እንዲቆሙ ያደረጉ እጅግ የሚያስጨንቁ የሲቃ ጩኸቶች፡፡ ከዚያ በኋላ አሰቃቂዎቹ ንዴት የሚንጸባረቅባቸው ድምጾች መጡ፣ ‹‹ግደሏቸው! ግደሏቸው! ሁሉንም ግደሏቸው!››
ብዙ መጯጯህና የድረሱልኝ ጥሪ ይሰማል፤ ‹‹ግደለው! ግደሉት! ግደላት!›› የሚልም ድምፅ ይከተላል፡፡
ፈራን፡፡ ከሴቶቹ አብዛኞቹ መሬት ላይ ተኙ፣ አልጋም ስር ተደበቁ፡፡ በጣም ከመንዘፈዘፌ የተነሣ መሬቱም ጭምር የሚንቀጠቀጥ መሰለኝ፡፡ ዓይኖቼ ቤቱን መደበቂያ ፍለጋ ሲያስሱ በኮርኒሱ ላይ ባለች አንዲት ቀዳዳ ላይ አተኮሩ፡፡
‹‹እዚያ ላይ መደበቅ እንችላለን›› አልኩ ወንበር ወደ ቀዳዳዋ ስር እየሳብኩና በእጆቼ ወደላይ እየተንጠራራሁ፡፡ አንዷን ሴትዮ ወደ ላይ ስቤ አወጣኋት፡፡ ሁለታችን ደግሞ አንድ ላይ ሌሎቹን በቀዳዳዋ ሽቅብ ሳብናቸው፡፡ ከዚያም ቄሱን እስኪመለሱ እንጠብቃቸው ያዝን፡፡ በዚያች በተጨናነቀችና በምታፍን ቦታ ልብሶቻችን በላብ እስኪጠመቁና አየር እስኪያጥረን ድረስ ጭብጥ ብለን ተቀመጥን፡፡ ቄስ ሙሪንዚ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ተመልሰው በቤቱ መካከል ቆመው ራሳቸውን በግራ-ግባት ያኩ ገቡ፡፡
‹‹የት ይሆኑ? አይ አምላኬ እዚህ ነበር የተውኳቸው!››
በጣም ባልፈራ ኖሮ ሳቄን እለቀው ነበር፡፡ በቀዳዳዋ ራሴን አውጥቼ ‹‹እዚህ ነን!›› ስል አንሾካሾክሁ፡፡
ቄሱ ራሳቸውን ነቅንቀው ሊያናግሩን መፈለጋቸውን ገልጸውልን ወዲያውኑ እንድንወርድ አዘዙን፡፡ ፊታቸው አሁንም በጣም እንደተቸገሩ ያስታውቃል፡፡ ‹‹ሁላችሁም እንደፈራችሁ አውቃለሁ፤ በእርግጥ ልትፈሩም ይገባችኋል›› አሉን፡፡ ‹‹ውጪ ላይ ነገሩ ሁሉ ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል፡፡ ገዳዮቹ በሁሉም ሰው ቤት እየዞሩ ነው፡፡ ዛሬ እኔ ቤት አልመጡም፤ በማናቸውም ሰዓት ግን ሊመጡ ይችላሉ፡፡ እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ምን እንደማደርጋችሁ አላውቅም… እስኪ ላስብበት፡፡››
ፍራቻችንን አይተው ወዲያውኑ መፍትሔ አመጡ፡፡ ‹‹አይዟችሁ አላስወጣችሁም›› ሲሉ አረጋገጡልን፡፡ እስኪ በጥሞና አዳምጡኝ፡፡ ነገ ሲነጋጋና ማንም ከመኝታው ሳይነሳ ግድያው እስኪያቆም ድረስ ወደምትቆዩበት አንድ ሌላ ክፍል እወስዳችኋለሁ፡፡ በቤቱ ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዳስወጣኋችሁ እነግራቸዋለሁ፡፡ የእናንተን እዚህ መኖር የማውቀው ብቸኛ ሰው እኔ ብቻ እሆናለሁ፡፡ ተራ ሐሜት እንኳን ሁላችንንም ሊያስገድለን ይችላል፡፡ እነዚህን የግድያ ዘመቻዎች ካሁን በፊት አይቻቸዋለሁ - አንዴ የደም ጥማቱ ከጀመረ ማንንም አታምኑም፣ የራሳችሁንም ልጆች ሳይቀር፡፡ አንድ ሰው ካገኛችሁ አለቀላችሁ! ስለዚህ በእግዚአብሔር ደማችሁ በቤቴም ሆነ በጄ እንዲፈስ አልፈልግም፡፡››
ከዚያ ቄሱ ወደኔ ዞረው እንደ ቢላዋ የቆረጡኝን ቃላት ነገሩኝ - ‹‹ወንድምሽና ጓደኛው እዚህ መቆየት አይችሉም፡፡ አሁኑኑ ሄደው ሕይወታቸውን ያትርፉ፡፡ ወንዶችን ማስጠለል ለኔ በጣም አደገኛ ነው፡፡ እንደምታዪው እናንተ ሴቶቹም በዝታችሁብኛል፡፡››
በሙሉ ዓይናቸው ሊያዩኝ አልቻሉም - ቪያኒንና ኦገስቲንን በዚያ ሰዓት ማባረሩ በእርግጠኝነት ማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ወደ ሞታቸው መላክ ማለት እንደሆነ ሁለታችንም እናውቃለን፡፡
‹‹እንዴ! ቄስ ሙሪንዚ ኧረ እባክዎት! እንዴት -››
ጸጥ በይ በሚል ዓይነት ምልክት ጣታቸውን ከንፈራቸው ላይ አድርገው ንግግራችንን ቋጩት፡፡ ‹‹መሄድ አለባቸው፣ ኢማኪዩሌ፡፡ ልወስዳችሁ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ስመጣ ወደ በሩ ወስደሽ ታስወጫቸዋለሽ፡፡ ታዲያ ማንም እንዳያይሽ ተጠንቀቂ፡፡››
ቄሱ ቤቱን ለቀው ሲሄዱ በሹክሹክታ ረገምኳቸው፡፡ ለኛ ከለላ በመስጠት እንደ ቅዱስ እየሰሩ እንዴት እንደገና ተገልብጠው ወንድሜንና ኦገስቲንን ወደ ገዳዮቹ እጆች ያስገቧቸዋል?
እያዳኑን የነበሩትን ሰው ልቆጣቸው አልፈለግሁም፣ ቢሆንም ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም - የባሰውንም ጠረጠርኩ፡፡ በሌሎች የግድያ ዘመቻዎች አንዳንድ የሁቱ ወንዶች ወንድ ቱትሲዎችን ትተው ሴት ቱትሲዎችን
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ልጆቹን_ስሰናበት
፡
ዳማሲን ከመሄዱ የቄሱ ግቢ የፊት በር ተንኳኳ፡፡ ያንኳኳው የቪያኒ የሁለተኛ ደረጃ መምህር የሆነው ንዚማ ሲሆን አመጣጡም ቄስ ሙሪንዚን ፈልጎ ነው፡፡ የሹክሹክታ ንግግር ከተደረገ በኋላ በሩ ተዘጋ፡፡ ወጥቼ ንዚማን በቄሱ ዛፍ ጥላ ስር ተቀምጦ አገኘሁት፡፡ በዚያ ደብዘዝ ባለው ብርሃንም ቢሆን በፊቱ ላይ የሚነበበውን ህመም ማየት አይከብድም፡፡
እንደፈራ ልጅ አድርጎታል - ‹‹ምን ያደርጉናል? የሚገድሉን ይመስልሻል?›› ሲል ጠየቀኝ፡፡
በሩ ጋ መምጣቱን እንደሰማሁ በራስ ወዳድነት ስሜት ተውጬ የማበረታቻ ቃላት ይሰነዝርልኝና ጥንካሬ ይለግሰኝ ዘንድ ተመኝቻለሁ፤ ግን እርሱ ነው ሁለቱንም ላያገኛቸው ይሻቸው የያዘው፡፡
መምህር ንዚማ ሚስትና ልጆቹ ራቅ ባለ መንደር አማቱን ሊጠይቁ ሄደዋል፡፡ ደኅና ስለመሆናቸው ምንም የሚያውቅበት መንገድ ስላጣና ጥርጣሬ ስለገባው ተሰቃየ፡፡ ‹‹የማልተዋቸው ህልሞች አሉኝ›› አለ፡፡ ‹‹ሚስቴና ልጆቼ ሲታረዱና እፊቴ ሲቆራረጡ ይታየኛል፡፡ ይህን ለማስቆም እንደምታዪኝ ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ በአሁኑ ሰዓት እኮ ተገድለው መንገድ ላይ ተጥለው ነው የሚሆነው፡፡›› በቻልኩት መጠን ላጽናናው ሞከርኩ፤ ግን ምን ልለው እችላለሁ? እኔ ራሴ እርግጠኛ ባልሆንኩበት ሁኔታ ነገሮች ጥሩ ሊሆኑ እንደሚችሉ ስንት ጊዜ ልናገር?
በጣም አቃሰተና ‹‹የት አባቴ ልግባ? ውጪ ያለው ሁሉም ሰው ገጀራ ይዟል፤ ጠመንጃ የያዙም አይቻለሁ፡፡››
‹‹ግድያው እስኪያቆም ድረስ እዚህ ቆያ፤ ከዚያም ከቤተሰብህ ትገናኛለህ›› አልኩት መንፈሱን ለማረጋጋት፡፡
ራሱን ነቅንቆ ቆመና ‹‹ልጄ፣ እዚህ አልቆይም፤ ሌላ የምሄድበት ቦታም የለኝ፡፡››
‹‹እጸልይልሃለሁ፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ ኢማኪዩሌ፡፡››
ተሰናብቶኝ ቄስ ሙሪንዚ ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ቤቱ ፊት ለፊት ሄደ፡፡ ቄሱ ንዚማን እንደማይሸሽጉት ነግረውት ሳይሆን አይቀርም በሩን በእጃቸው ሲያመላክቱት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ወጣ፡፡ በኋላ እንደሰማሁት ይህ ምስኪን ሰው ተቆራርጦ የተገደለው ከቄሱ ቤት ጥቂት መቶ ሜትሮች ርቆ ባለ መንገድ ላይ ነው፡፡ ከተወሰኑ ሰዓታት በኋላ ብቻዬን በተቀመጥኩባት በአንዲት ትንሽ መኝታ ክፍል ቄስ ሙሪንዚ ሌሎች አምስት ቱትሲ ሴቶችን በጸጥታ አስገቡ፡፡ ሁሉም የአካባቢያችን ሰዎች እንደሆኑ ባውቅም አንዳቸውንም በደንብ አላወቅኋቸውም፡፡ ሴቶቹን ወደ ክፍሏ ሲያመጧቸው ቄሱ ተደናግጠዋል፡፡ ‹‹ፍጠኑ፣ ፍጠኑ!›› የሚንሾካሾኩት በጣም በፍጥነት ስለሆነ ልንሰማቸው አልቻልንም፡፡ ‹‹እዚህ ጠብቁኝ፤ ታዲያ ደሞ ዝም በሉ እሺ›› አሉን በሩን ዘግተው ሲወጡ፡፡ አብረን የነበርነው ስድስት ቱትሲ ሴቶች ከሞላ ጎደል እርስ በርስ የማንተዋወቅ ቢሆንም ሁለት ነገሮች ግን ያመሳስሉናል - እየታደንን መሆናችንና የምንደበቅበት ምንም ስፍራ የሌለን መሆኑ፡፡ ለመናገርም ሆነ ለመተዋወቅ በጣም ፈርተን እርስ በርሳችን እየተያየን ቆመናል፡፡ ውጪ ምን እየተከሰተ እንዳለ አናውቅም፣ ከቄሱ ድንጋጤ እንደተረዳነው ግን ነገሮች ተበለሻሽተዋል፡፡
ከቤቱ ውጪ ድንገት ጩኸቶች ይሰሙ ጀመር - በእጆቻችን ላይ ያሉትን ጸጉሮች እንዲቆሙ ያደረጉ እጅግ የሚያስጨንቁ የሲቃ ጩኸቶች፡፡ ከዚያ በኋላ አሰቃቂዎቹ ንዴት የሚንጸባረቅባቸው ድምጾች መጡ፣ ‹‹ግደሏቸው! ግደሏቸው! ሁሉንም ግደሏቸው!››
ብዙ መጯጯህና የድረሱልኝ ጥሪ ይሰማል፤ ‹‹ግደለው! ግደሉት! ግደላት!›› የሚልም ድምፅ ይከተላል፡፡
ፈራን፡፡ ከሴቶቹ አብዛኞቹ መሬት ላይ ተኙ፣ አልጋም ስር ተደበቁ፡፡ በጣም ከመንዘፈዘፌ የተነሣ መሬቱም ጭምር የሚንቀጠቀጥ መሰለኝ፡፡ ዓይኖቼ ቤቱን መደበቂያ ፍለጋ ሲያስሱ በኮርኒሱ ላይ ባለች አንዲት ቀዳዳ ላይ አተኮሩ፡፡
‹‹እዚያ ላይ መደበቅ እንችላለን›› አልኩ ወንበር ወደ ቀዳዳዋ ስር እየሳብኩና በእጆቼ ወደላይ እየተንጠራራሁ፡፡ አንዷን ሴትዮ ወደ ላይ ስቤ አወጣኋት፡፡ ሁለታችን ደግሞ አንድ ላይ ሌሎቹን በቀዳዳዋ ሽቅብ ሳብናቸው፡፡ ከዚያም ቄሱን እስኪመለሱ እንጠብቃቸው ያዝን፡፡ በዚያች በተጨናነቀችና በምታፍን ቦታ ልብሶቻችን በላብ እስኪጠመቁና አየር እስኪያጥረን ድረስ ጭብጥ ብለን ተቀመጥን፡፡ ቄስ ሙሪንዚ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ተመልሰው በቤቱ መካከል ቆመው ራሳቸውን በግራ-ግባት ያኩ ገቡ፡፡
‹‹የት ይሆኑ? አይ አምላኬ እዚህ ነበር የተውኳቸው!››
በጣም ባልፈራ ኖሮ ሳቄን እለቀው ነበር፡፡ በቀዳዳዋ ራሴን አውጥቼ ‹‹እዚህ ነን!›› ስል አንሾካሾክሁ፡፡
ቄሱ ራሳቸውን ነቅንቀው ሊያናግሩን መፈለጋቸውን ገልጸውልን ወዲያውኑ እንድንወርድ አዘዙን፡፡ ፊታቸው አሁንም በጣም እንደተቸገሩ ያስታውቃል፡፡ ‹‹ሁላችሁም እንደፈራችሁ አውቃለሁ፤ በእርግጥ ልትፈሩም ይገባችኋል›› አሉን፡፡ ‹‹ውጪ ላይ ነገሩ ሁሉ ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል፡፡ ገዳዮቹ በሁሉም ሰው ቤት እየዞሩ ነው፡፡ ዛሬ እኔ ቤት አልመጡም፤ በማናቸውም ሰዓት ግን ሊመጡ ይችላሉ፡፡ እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ምን እንደማደርጋችሁ አላውቅም… እስኪ ላስብበት፡፡››
ፍራቻችንን አይተው ወዲያውኑ መፍትሔ አመጡ፡፡ ‹‹አይዟችሁ አላስወጣችሁም›› ሲሉ አረጋገጡልን፡፡ እስኪ በጥሞና አዳምጡኝ፡፡ ነገ ሲነጋጋና ማንም ከመኝታው ሳይነሳ ግድያው እስኪያቆም ድረስ ወደምትቆዩበት አንድ ሌላ ክፍል እወስዳችኋለሁ፡፡ በቤቱ ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዳስወጣኋችሁ እነግራቸዋለሁ፡፡ የእናንተን እዚህ መኖር የማውቀው ብቸኛ ሰው እኔ ብቻ እሆናለሁ፡፡ ተራ ሐሜት እንኳን ሁላችንንም ሊያስገድለን ይችላል፡፡ እነዚህን የግድያ ዘመቻዎች ካሁን በፊት አይቻቸዋለሁ - አንዴ የደም ጥማቱ ከጀመረ ማንንም አታምኑም፣ የራሳችሁንም ልጆች ሳይቀር፡፡ አንድ ሰው ካገኛችሁ አለቀላችሁ! ስለዚህ በእግዚአብሔር ደማችሁ በቤቴም ሆነ በጄ እንዲፈስ አልፈልግም፡፡››
ከዚያ ቄሱ ወደኔ ዞረው እንደ ቢላዋ የቆረጡኝን ቃላት ነገሩኝ - ‹‹ወንድምሽና ጓደኛው እዚህ መቆየት አይችሉም፡፡ አሁኑኑ ሄደው ሕይወታቸውን ያትርፉ፡፡ ወንዶችን ማስጠለል ለኔ በጣም አደገኛ ነው፡፡ እንደምታዪው እናንተ ሴቶቹም በዝታችሁብኛል፡፡››
በሙሉ ዓይናቸው ሊያዩኝ አልቻሉም - ቪያኒንና ኦገስቲንን በዚያ ሰዓት ማባረሩ በእርግጠኝነት ማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ወደ ሞታቸው መላክ ማለት እንደሆነ ሁለታችንም እናውቃለን፡፡
‹‹እንዴ! ቄስ ሙሪንዚ ኧረ እባክዎት! እንዴት -››
ጸጥ በይ በሚል ዓይነት ምልክት ጣታቸውን ከንፈራቸው ላይ አድርገው ንግግራችንን ቋጩት፡፡ ‹‹መሄድ አለባቸው፣ ኢማኪዩሌ፡፡ ልወስዳችሁ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ስመጣ ወደ በሩ ወስደሽ ታስወጫቸዋለሽ፡፡ ታዲያ ማንም እንዳያይሽ ተጠንቀቂ፡፡››
ቄሱ ቤቱን ለቀው ሲሄዱ በሹክሹክታ ረገምኳቸው፡፡ ለኛ ከለላ በመስጠት እንደ ቅዱስ እየሰሩ እንዴት እንደገና ተገልብጠው ወንድሜንና ኦገስቲንን ወደ ገዳዮቹ እጆች ያስገቧቸዋል?
እያዳኑን የነበሩትን ሰው ልቆጣቸው አልፈለግሁም፣ ቢሆንም ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም - የባሰውንም ጠረጠርኩ፡፡ በሌሎች የግድያ ዘመቻዎች አንዳንድ የሁቱ ወንዶች ወንድ ቱትሲዎችን ትተው ሴት ቱትሲዎችን
👍1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_ስምንት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ቁጣዬን_ስጋፈጥ
፡
፡
በአንጻራዊ መረጋጋት በርካታ ቀናት አለፉ፡፡ አልፎ አልፎ ገዳዮቹ ውጪ ላይ የእብድ መዝሙራቸውን ሲዘምሩ እንሰማቸዋለን፡፡ ቀኑን ሙሉ በጽሞና እንጸልያለን፤ እርስ በርሳችንም በምልክት ቋንቋ እንግባባለን፡፡ ከሞላ ጎደል በየ12 ሰዓታቱ የተወሰኑ ተናፋቂ የሰውነት ማፍታቻዎችን እናደርጋለን፡፡ ከዚያ በስተቀረ ቀንና ሌሊት በአንድ ቦታ በመቀመጥ እንቅስቃሴዎቻችንን በተቻለን መጠን እንገድባለን፡፡ መጸዳጃ ቤቱን በቄስ ሙሪንዚ ትዕዛዝ መሠረት ውሃ እንለቅበታለን፡፡ ይህም ሌላ ሰው በዋናው ቤት ውስጥ ያለውን ሌላውን መጸዳጃ ቤት ውሃ ሲለቅበት መሆኑ ነው፡፡ መጸዳጃውን መጠቀሙ ፈተና ሆነብን፡፡ ስፍራው በቂ ስላልሆነ የምትጠቀመው ሰው ከእብነበረድ በተሰራው መጸዳጃ ላይ ቁጢጥ ለማለት ትገደዳለች፤ ስለሆነም አንደኛችን ስንጸዳዳ ሁላችንም ቦታ መቀያየር አለብን፡፡ ያም ድምፅ የማሰማትና በገዳዮቹ የመገኘት አደጋን ጋርጦብናል፡፡
ባልተለመደ ሁኔታ በመታጠቢያ ቤቱ በቆየንበት ጊዜ ማንም መጸዳጃውን ሲጠቀም ማየቴን አላስታውስም፡፡ መጸዳጃው ከእብነበረድ የተሠራና እላዩ ላይ አስቀምጦ የሚያጸዳዳው ዓይነቱ ነው፡፡ ያለው በዚያች ትንሽ ቦታ መካከል ቢሆንም ሽታው ያስቸገረኝ ወቅት ትዝም አይለኝ፡፡ የወር አበባችንም ይደርሳል፤ ያንዳችን ሲሄድ የሌላችን ከተፍ ይላል፡፡ በመሆኑም ቄሱን ተጨማሪ የንጽሕና መጠበቂያ ወረቀት አምጡ እያልን እናስቸግራቸዋለን፡፡ ማንኛችንም ብንሆን ባለው ሁኔታ አንሸማቀቅም፤ እነዚህን ሁኔታዎች ረስተናቸዋል፤ የብቸኝነትም ጥሩ ጎኖች ትዝ አይሉን፤ በተለይ ይህ ችግር በሕይወት ከመኖራችን አንጻር ሲታይ ከግምት ውስጥ አይገባምና፡፡
ቄሱ ምግብ ይዘው በመጡ ቁጥር እንበላለን - የሚያመጡልን አልፎ አልፎ ቢሆንም፡፡ አንዳንድ ቀንማ ያለ ሌሊት 9 ወይንም 10 ሰዓት አይመጡም፡፡ (ሊያዩን ወይንም ምግብ ሊያመጡልን በፈለጉ ቁጥር ቁምሳጥኑን ገፍተው ይገባሉ፡፡ ሁልጊዜ ግን ሌላ ሰው እንዳይሰማቸው በጣም ይጠነቀቃሉ፡፡ ከቁምሳጥኑ ሲንቀሳቀስ ድምጹን ለማፈን የሚሆን ጨርቅ ከስሩ ተደርጎበታል፡፡ በዚህም እግዚአብሔር እንደገና ይጠብቀን ይዟል፡፡) ተጨማሪ ምግብ ቢያዘጋጁ ሌላ ሰው እንዳያውቅባቸው የልጆቻቸውን ትርፍራፊ ወይንም ሠራተኞቻቸው የሚበሉትን አሸር ባሸር ያመጡልናል፡፡ አንዳንዴ ምንም ብንራብም አንበላም እንላለን - የሚሰጡን የአሳማ ምግብ ይመስላላ፡፡ (እቤቴ ምን ዓይነት ምግብ አማራጭ እንደነበርኩ በማስታወስ በራሴ ላይ እሥቃለሁ፡፡) የምንጠጣውም ውሃ ይመጣልናል፡፡
የማይቻል ቢመስልም ከቀናት ጸጥታ በኋላ ትንሽ ዘና አልን፡፡ ያለንበትን ሁኔታ የሚያስታውሱን ቄሱ ብቻ ናቸው፡፡
አንድ ሌሊት ቄሱ መጥተው ገዳዮቹ ባቅራቢያችን ከቤት ወደ ቤት በመዘዋወር ቤቶችን እየፈተሹ ያገኙትን ቱትሲም እየገደሉ እንደሆነ ነገሩን፡፡ ‹‹በተወሰኑ ደቂቃዎች ውስጥ ሊመጡ ይችላሉ፤ ምናልባትም እስከ ነገ ወይንም ከነግወዲያ ድረስም ላይመጡ ይችላሉ፡፡ በእርግጠኝነት ግን ይመጣሉ፤ ስለዚህም ዝም በሉ›› ሲሉ አስጠነቀቁን፡፡ በዚያች መታጠቢያ ቤት ውስጥ ትንሽ የአእምሮ ሰላም ለማግኘት የነበረን ተስፋ ተነነ፡፡ ስለገዳዮቹ መመለስ ያደረብን ሥጋት አዕምሯዊና አካላዊ ውጋት ሆነብን፡፡ ወለሉ ላይ ድምፅ በሰማሁና ዉሻ በጮኸ ቁጥር አንድ ሰው በስለት እንደወጋኝ ይሰማኛል፡፡ በአንዴ መተኛት የምንችለው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ስለሆነ ቆዳዬ መድረቅና መላጥ አመጣ፡፡ ሁልጊዜም የማይተወኝ ራስ ምታትም ይዞኝ ተቸገርኩ፡፡ የአእምሮ ሥቃዬማ እንዲያውም በጣም ያይላል፡፡ በሃሳቤ ወጥመድ ውስጥ ብቻዬን እሰቃያለሁ፡፡ ከደረስኩ ጀምሮ የሚያስቸግሩኝ ጽኑ ፍርሃቶችና ቅዠቶች በልቤ ውስጥ እየተመላለሱ የእምነቴን መሠረት አናጉት፡፡ ገዳዮቹ ድምጻቸው ለኛ በሚሰማን ርቀት ሲጠጉ ሐሳቤ ከፈጣሪ ራቀና በአሉታዊው ሐሳብ ተጠመድኩ፡፡ በጸለይኩ ቁጥር ግን ወዲያውኑ ፍቅሩን አገኘዋለሁ፤ ስጋቴም ይቀልልኛል፡፡
ስለዚህ ሌሊት ከ10 ወይም 11 ሰዓት ጀምሬ በማንኛዋም እንቅልፍ ባልያዘኝ ሰዓት ለመጸለይ ወሰንኩ፡፡ ሁልጊዜ የመጀመሪያ ጸሎቴ የቄሱ ቤት ስለተሠራልንና በዘር ጭፍጨፋው ወቅት ስለተጠለልንበት አምላክን ማመስገን ነው፡፡ ከዚያም የቤቱ ንድፍ-አውጪ ከተጨማሪ መታጠቢያ ቤት ጋር እንዲነድፈው ስላደረገው፣ ብሎም ለቄሱ የኛን መደበቂያ ስፍራ መሸፈኛ የሚሆን ልከኛ ቁምሣጥን እንዲገዙ ስለገፋፈ
ወቸው አመሰግነዋለሁ፡፡
ከመጀመሪያው የምስጋና ጸሎቴ በኋላ በመቁጠሪያዬ መጸለይ እጀምራለሁ፡፡ ጸሎቶችን በቀዮቹና ነጮቹ ዶቃዎች አደርሳለሁ፡፡ አንዳንዴ በጣም ስለምጸልይ ያልበኛል፡፡ ሰዓታትም ያልፋሉ… ዶቃዎቹንና ጸሎቴን ስጨርስ የምወዳቸውን
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በማለት ‹‹እረፍት›› አደርጋለሁ፡፡ እምነቴ በአደጋ ላይ እንደወደቀ ስለማስብ ከማርቆስ ወንጌል የማስታውሳቸውን ስለ እምነት ጉልበት የሚያወሱ ሁለት ጥቅሶች በመደጋገም ሰዓታትን አሳልፋለሁ፡፡ መጀመሪያ ይህ ነው - ‹‹ስለዚህም እላችኋለሁ፣ አምናችሁ ብትፀልዩ የምትለምኑትን ሁሉ ታገኛላችሁ፤ ይሆንላችሁማል›› (ማርቆስ 11፡ 24)፡፡ ከዚያም ሌላውን እላለሁ - ‹‹እውነት እላችኋለሁ፣ ይህን ተራራ ተነሥተህ ወደ ባህር ተወርወር ብትሉት፣ በልባችሁም ባትጠራጠሩ፣ ብታምኑም እንደተናገራችሁት ይሆናል›› (ማርቆስ 11፡23)፡፡ ሳልጸልይና ስለ እግዚአብሔር ሳላስብ የማሳልፋት ጥቂት ደቂቃ እንኳን ብትኖር ሰይጣን መንታ ጫፍ ባለው የጥርጣሬና በራስ የማዘን ቢላዋው ይወጋኝ ዘንድ መጋበዝ ይሆናል፡፡ ጸሎት መከላከያዬ በመሆኑ ልቤን አጥብቄ እጠቀልልበታለሁ፡፡
ቄሱ ሁልጊዜ ያልሆነ ስህተት ሰርተን ድምፅ እንዳናሰማ ይፈራሉ፡፡ ስለሆነም ወደ መኝታ ክፍላቸው ሰው የሚያመጡት እጅግ አልፎ አልፎ ነው፡፡ አንዳንዴ ግን ከልጆቻቸው አንዷ ወይንም አስተናጋጃቸው ሊጠይቋቸው ሲመጡ እስኪሄዱ ድረስ እንደነዝዛለን፡፡ እዚህ ከመጣን ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ ቄሱ ከልጃቸው ከሴምቤባ ጋር ሲያወሩ ሰማናቸው፡፡
‹‹አባባ፣ ስለዚህ ግድያ ምን ትላለህ? ጥሩ አይመስልህም - እኛ ሁቱዎች ማድረግ ያለብን ትክክለኛው ነገር አይመስልህም? ማለቴ በትምህርት ቤት ሲያስተምሩን ከመቶዎች ዓመታት በፊት ቱትሲዎች በእኛ ላይ ተመሳሳይ ነገር አድርሰዋል፤ ስለዚህ እያገኙት ያለው ነገር ይገባቸዋል አይደል?››
‹‹ሴምቤባ ስለምን እያወራህ እንደሆነ አታውቅም፡፡ በል ተወኝ አሁን፤ ልተኛበት›› ሲሉ መለሱ ቄሱ፡፡
‹‹ቱትሲዎች ሲባሉ ሁልጊዜ የበላይ ነን ብለው ያስባሉ… ሁሌ ሁቱዎችን ዝቅ አድርገው ያዩናል፡፡ ዛሬም ድረስ ሥልጣን ላይ ቢሆኑ ኖሮ አሁን እየገደሉን አይሆንም ነበር? ስለዚህ እነርሱን መግደል ራስን መከላከል ነው፣ አይደለም?›› ድምጹ በጣም በመጉላቱ ሴምቤባ ቁምሳጥኑ ጎን እንደቆመ መገመት እችላለሁ፡፡ የቁምሳጥኑንም መንቀሳቀስ ያውቅብናል ብዬ በጣም ተሸበርኩ፡፡ እንደፈራሁም ቢሆን ተነሥቼ ልጩህበት የሚለውን ሃሳቤን መቋቋም ነበረብኝ - ቃላቱ በጣም አናደዱኝ፡፡ ይህን ለቱትሲዎች ያለውን ንቀት የተማረው በትምህርት ቤት እንደሆነ ስለማውቅና እኔም እዚያ ትምህርት ቤት ስለተማርኩ ለድንቁርናው ብቸኛው ተጠያቂ እንዳልሆነ ይገባኛል! ወጣት ሁቱዎች ከልጅነታቸው ጀምሮ ቱትሲዎች የበታችና
፡
፡
#ምዕራፍ_ስምንት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ቁጣዬን_ስጋፈጥ
፡
፡
በአንጻራዊ መረጋጋት በርካታ ቀናት አለፉ፡፡ አልፎ አልፎ ገዳዮቹ ውጪ ላይ የእብድ መዝሙራቸውን ሲዘምሩ እንሰማቸዋለን፡፡ ቀኑን ሙሉ በጽሞና እንጸልያለን፤ እርስ በርሳችንም በምልክት ቋንቋ እንግባባለን፡፡ ከሞላ ጎደል በየ12 ሰዓታቱ የተወሰኑ ተናፋቂ የሰውነት ማፍታቻዎችን እናደርጋለን፡፡ ከዚያ በስተቀረ ቀንና ሌሊት በአንድ ቦታ በመቀመጥ እንቅስቃሴዎቻችንን በተቻለን መጠን እንገድባለን፡፡ መጸዳጃ ቤቱን በቄስ ሙሪንዚ ትዕዛዝ መሠረት ውሃ እንለቅበታለን፡፡ ይህም ሌላ ሰው በዋናው ቤት ውስጥ ያለውን ሌላውን መጸዳጃ ቤት ውሃ ሲለቅበት መሆኑ ነው፡፡ መጸዳጃውን መጠቀሙ ፈተና ሆነብን፡፡ ስፍራው በቂ ስላልሆነ የምትጠቀመው ሰው ከእብነበረድ በተሰራው መጸዳጃ ላይ ቁጢጥ ለማለት ትገደዳለች፤ ስለሆነም አንደኛችን ስንጸዳዳ ሁላችንም ቦታ መቀያየር አለብን፡፡ ያም ድምፅ የማሰማትና በገዳዮቹ የመገኘት አደጋን ጋርጦብናል፡፡
ባልተለመደ ሁኔታ በመታጠቢያ ቤቱ በቆየንበት ጊዜ ማንም መጸዳጃውን ሲጠቀም ማየቴን አላስታውስም፡፡ መጸዳጃው ከእብነበረድ የተሠራና እላዩ ላይ አስቀምጦ የሚያጸዳዳው ዓይነቱ ነው፡፡ ያለው በዚያች ትንሽ ቦታ መካከል ቢሆንም ሽታው ያስቸገረኝ ወቅት ትዝም አይለኝ፡፡ የወር አበባችንም ይደርሳል፤ ያንዳችን ሲሄድ የሌላችን ከተፍ ይላል፡፡ በመሆኑም ቄሱን ተጨማሪ የንጽሕና መጠበቂያ ወረቀት አምጡ እያልን እናስቸግራቸዋለን፡፡ ማንኛችንም ብንሆን ባለው ሁኔታ አንሸማቀቅም፤ እነዚህን ሁኔታዎች ረስተናቸዋል፤ የብቸኝነትም ጥሩ ጎኖች ትዝ አይሉን፤ በተለይ ይህ ችግር በሕይወት ከመኖራችን አንጻር ሲታይ ከግምት ውስጥ አይገባምና፡፡
ቄሱ ምግብ ይዘው በመጡ ቁጥር እንበላለን - የሚያመጡልን አልፎ አልፎ ቢሆንም፡፡ አንዳንድ ቀንማ ያለ ሌሊት 9 ወይንም 10 ሰዓት አይመጡም፡፡ (ሊያዩን ወይንም ምግብ ሊያመጡልን በፈለጉ ቁጥር ቁምሳጥኑን ገፍተው ይገባሉ፡፡ ሁልጊዜ ግን ሌላ ሰው እንዳይሰማቸው በጣም ይጠነቀቃሉ፡፡ ከቁምሳጥኑ ሲንቀሳቀስ ድምጹን ለማፈን የሚሆን ጨርቅ ከስሩ ተደርጎበታል፡፡ በዚህም እግዚአብሔር እንደገና ይጠብቀን ይዟል፡፡) ተጨማሪ ምግብ ቢያዘጋጁ ሌላ ሰው እንዳያውቅባቸው የልጆቻቸውን ትርፍራፊ ወይንም ሠራተኞቻቸው የሚበሉትን አሸር ባሸር ያመጡልናል፡፡ አንዳንዴ ምንም ብንራብም አንበላም እንላለን - የሚሰጡን የአሳማ ምግብ ይመስላላ፡፡ (እቤቴ ምን ዓይነት ምግብ አማራጭ እንደነበርኩ በማስታወስ በራሴ ላይ እሥቃለሁ፡፡) የምንጠጣውም ውሃ ይመጣልናል፡፡
የማይቻል ቢመስልም ከቀናት ጸጥታ በኋላ ትንሽ ዘና አልን፡፡ ያለንበትን ሁኔታ የሚያስታውሱን ቄሱ ብቻ ናቸው፡፡
አንድ ሌሊት ቄሱ መጥተው ገዳዮቹ ባቅራቢያችን ከቤት ወደ ቤት በመዘዋወር ቤቶችን እየፈተሹ ያገኙትን ቱትሲም እየገደሉ እንደሆነ ነገሩን፡፡ ‹‹በተወሰኑ ደቂቃዎች ውስጥ ሊመጡ ይችላሉ፤ ምናልባትም እስከ ነገ ወይንም ከነግወዲያ ድረስም ላይመጡ ይችላሉ፡፡ በእርግጠኝነት ግን ይመጣሉ፤ ስለዚህም ዝም በሉ›› ሲሉ አስጠነቀቁን፡፡ በዚያች መታጠቢያ ቤት ውስጥ ትንሽ የአእምሮ ሰላም ለማግኘት የነበረን ተስፋ ተነነ፡፡ ስለገዳዮቹ መመለስ ያደረብን ሥጋት አዕምሯዊና አካላዊ ውጋት ሆነብን፡፡ ወለሉ ላይ ድምፅ በሰማሁና ዉሻ በጮኸ ቁጥር አንድ ሰው በስለት እንደወጋኝ ይሰማኛል፡፡ በአንዴ መተኛት የምንችለው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ስለሆነ ቆዳዬ መድረቅና መላጥ አመጣ፡፡ ሁልጊዜም የማይተወኝ ራስ ምታትም ይዞኝ ተቸገርኩ፡፡ የአእምሮ ሥቃዬማ እንዲያውም በጣም ያይላል፡፡ በሃሳቤ ወጥመድ ውስጥ ብቻዬን እሰቃያለሁ፡፡ ከደረስኩ ጀምሮ የሚያስቸግሩኝ ጽኑ ፍርሃቶችና ቅዠቶች በልቤ ውስጥ እየተመላለሱ የእምነቴን መሠረት አናጉት፡፡ ገዳዮቹ ድምጻቸው ለኛ በሚሰማን ርቀት ሲጠጉ ሐሳቤ ከፈጣሪ ራቀና በአሉታዊው ሐሳብ ተጠመድኩ፡፡ በጸለይኩ ቁጥር ግን ወዲያውኑ ፍቅሩን አገኘዋለሁ፤ ስጋቴም ይቀልልኛል፡፡
ስለዚህ ሌሊት ከ10 ወይም 11 ሰዓት ጀምሬ በማንኛዋም እንቅልፍ ባልያዘኝ ሰዓት ለመጸለይ ወሰንኩ፡፡ ሁልጊዜ የመጀመሪያ ጸሎቴ የቄሱ ቤት ስለተሠራልንና በዘር ጭፍጨፋው ወቅት ስለተጠለልንበት አምላክን ማመስገን ነው፡፡ ከዚያም የቤቱ ንድፍ-አውጪ ከተጨማሪ መታጠቢያ ቤት ጋር እንዲነድፈው ስላደረገው፣ ብሎም ለቄሱ የኛን መደበቂያ ስፍራ መሸፈኛ የሚሆን ልከኛ ቁምሣጥን እንዲገዙ ስለገፋፈ
ወቸው አመሰግነዋለሁ፡፡
ከመጀመሪያው የምስጋና ጸሎቴ በኋላ በመቁጠሪያዬ መጸለይ እጀምራለሁ፡፡ ጸሎቶችን በቀዮቹና ነጮቹ ዶቃዎች አደርሳለሁ፡፡ አንዳንዴ በጣም ስለምጸልይ ያልበኛል፡፡ ሰዓታትም ያልፋሉ… ዶቃዎቹንና ጸሎቴን ስጨርስ የምወዳቸውን
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በማለት ‹‹እረፍት›› አደርጋለሁ፡፡ እምነቴ በአደጋ ላይ እንደወደቀ ስለማስብ ከማርቆስ ወንጌል የማስታውሳቸውን ስለ እምነት ጉልበት የሚያወሱ ሁለት ጥቅሶች በመደጋገም ሰዓታትን አሳልፋለሁ፡፡ መጀመሪያ ይህ ነው - ‹‹ስለዚህም እላችኋለሁ፣ አምናችሁ ብትፀልዩ የምትለምኑትን ሁሉ ታገኛላችሁ፤ ይሆንላችሁማል›› (ማርቆስ 11፡ 24)፡፡ ከዚያም ሌላውን እላለሁ - ‹‹እውነት እላችኋለሁ፣ ይህን ተራራ ተነሥተህ ወደ ባህር ተወርወር ብትሉት፣ በልባችሁም ባትጠራጠሩ፣ ብታምኑም እንደተናገራችሁት ይሆናል›› (ማርቆስ 11፡23)፡፡ ሳልጸልይና ስለ እግዚአብሔር ሳላስብ የማሳልፋት ጥቂት ደቂቃ እንኳን ብትኖር ሰይጣን መንታ ጫፍ ባለው የጥርጣሬና በራስ የማዘን ቢላዋው ይወጋኝ ዘንድ መጋበዝ ይሆናል፡፡ ጸሎት መከላከያዬ በመሆኑ ልቤን አጥብቄ እጠቀልልበታለሁ፡፡
ቄሱ ሁልጊዜ ያልሆነ ስህተት ሰርተን ድምፅ እንዳናሰማ ይፈራሉ፡፡ ስለሆነም ወደ መኝታ ክፍላቸው ሰው የሚያመጡት እጅግ አልፎ አልፎ ነው፡፡ አንዳንዴ ግን ከልጆቻቸው አንዷ ወይንም አስተናጋጃቸው ሊጠይቋቸው ሲመጡ እስኪሄዱ ድረስ እንደነዝዛለን፡፡ እዚህ ከመጣን ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ ቄሱ ከልጃቸው ከሴምቤባ ጋር ሲያወሩ ሰማናቸው፡፡
‹‹አባባ፣ ስለዚህ ግድያ ምን ትላለህ? ጥሩ አይመስልህም - እኛ ሁቱዎች ማድረግ ያለብን ትክክለኛው ነገር አይመስልህም? ማለቴ በትምህርት ቤት ሲያስተምሩን ከመቶዎች ዓመታት በፊት ቱትሲዎች በእኛ ላይ ተመሳሳይ ነገር አድርሰዋል፤ ስለዚህ እያገኙት ያለው ነገር ይገባቸዋል አይደል?››
‹‹ሴምቤባ ስለምን እያወራህ እንደሆነ አታውቅም፡፡ በል ተወኝ አሁን፤ ልተኛበት›› ሲሉ መለሱ ቄሱ፡፡
‹‹ቱትሲዎች ሲባሉ ሁልጊዜ የበላይ ነን ብለው ያስባሉ… ሁሌ ሁቱዎችን ዝቅ አድርገው ያዩናል፡፡ ዛሬም ድረስ ሥልጣን ላይ ቢሆኑ ኖሮ አሁን እየገደሉን አይሆንም ነበር? ስለዚህ እነርሱን መግደል ራስን መከላከል ነው፣ አይደለም?›› ድምጹ በጣም በመጉላቱ ሴምቤባ ቁምሳጥኑ ጎን እንደቆመ መገመት እችላለሁ፡፡ የቁምሳጥኑንም መንቀሳቀስ ያውቅብናል ብዬ በጣም ተሸበርኩ፡፡ እንደፈራሁም ቢሆን ተነሥቼ ልጩህበት የሚለውን ሃሳቤን መቋቋም ነበረብኝ - ቃላቱ በጣም አናደዱኝ፡፡ ይህን ለቱትሲዎች ያለውን ንቀት የተማረው በትምህርት ቤት እንደሆነ ስለማውቅና እኔም እዚያ ትምህርት ቤት ስለተማርኩ ለድንቁርናው ብቸኛው ተጠያቂ እንዳልሆነ ይገባኛል! ወጣት ሁቱዎች ከልጅነታቸው ጀምሮ ቱትሲዎች የበታችና
👍2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_ዘጠኝ
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የማዋየው_ወዳጅ_ሳጣ
፡
በመታጠቢያ ቤቱ ውስጥ የራሴ የምለው ስፍራ እግኝቻለሁ - የልቤን ትንሽ ጥጋት፡፡ ስነቃ ወዲያውኑ ወደዚያ አፈገፍጋለሁ፤ እስክተኛ ድረስም በዚያው እቆያለሁ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የምነጋገርበት፣ ቃሉን የማሰላስልበትና መንፈሳዊ ማንነቴን የምንከባከብበት የተቀደሰ ስፍራዬ ነው፡፡
በምመሰጥበት ወቅት ከእምነቴ ምንጭ ደርሼ ነፍሴን አጠናክራለሁ፡፡ ሽብር ሲከበኝ በጎበኘሁት ቁጥር በሚያስደተኝና ነይ ነይ በሚለኝ ዓለም ከለላ አገኛለሁ፡፡ ሰውነቴ ሲንኮታኮት እንኳን ነፍሴ ከእግዚአብሔር ጋር ባለኝ የጠለቀ ግንኙነት ትፋፋለች::
ወደ ልዩ ስፍራዬ በጸሎት እገባለሁ፤ አንዴም ከገባሁ በኋላም ያለ ማቋረጥ እጸልያለሁ፣ መቁጠሪያዬን ሃሳቤንና ሃይሌን ወደ እግዚአብሔር እንዳተኩር እንደመልህቅ እጠቀመዋለሁ፡፡ የመቁጠሪያው ዶቃዎች በወንጌል ላይ እንዳተኩርና የእግዚአብሔርን ቃል በአእምሮዬ ህያው አድርጌ እንዳቆይ ረድተውኛል፡፡ በጸጥታ እጸልያለሁ፤ ግን ራሴን በእውነት እያልኳቸው እንደሆነ ለማሳመን ሁልጊዜ ቃላቱን በአፌ ድምፅ ሳላሰማ እላቸዋለሁ… ያ ባይሆን ኖሮ ጥርጣሬ ይገባኝና አሉታዊው ኃይል እየተጣራ ይመጣብኛል፡፡
የአንድን ነጠላ ቃል ትርጉም ሳሰላስል ሰዓታትን እወስዳለሁ፣ እንደ ምኅረት፣ እምነት ወይም ተስፋ ያሉትን፡፡ እጅ መስጠት የሚለውን ቃል ሳሰላስል ቀናትን አሳልፌያለሁ፡፡ በዚህም ምክንያት የራስን ስብዕና ለአንድ ከፍ ላለ ኃይል መስጠት ማለት ምን ማለት እንደሆነ ተረዳሁ፡፡ ራሴን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር አሳልፌ ሰጠሁ፡፡ በማልጸልይበት ጊዜ በእርሱ ብርሃን ውስጥ እንዳልሆንኩ ይሰማኛል፤ የመታጠቢያ ክፍሉ ዓለምም በበኩሉ ለመቋቋም የሚከብድ ነው፡፡ በተደበቅንበት የመጀመሪያው ወር መጨረሻ አካባቢ ቄስ ሙሪንዚ አንድ ሌሊት ላይ በጣም አምሽተው ትርፍራፊ ምግብ ይዘውልን መጡ፡፡ ወደዚህ ሲያስገቡን በሃዘኔታ ስሜት ቢሆንም አሁን ግን ያ እየጠፋ የሄደ መሰለ፡፡ በዚህ ምሽት ፊታቸው ከወትሮው የአሳቢነትና የሃዘኔታ ገጽታ ወደ መኮሳተር መጣ፡፡ ‹‹አባትሽ በጣም መጥፎ ቱትሲ ነበር!›› ሲሉ አያገጣብሩኝም!
‹‹ምን? ምን ማለትዎ ነው?›› ሙሉ በሙሉ የማደርገውን አሳጣኝ፤ ቢሆንም ግን በአባቴ ላይ የሰነዘሩት ጥቃት አባቴን ባለፈ ጊዜ የመግለጻቸውን ያህል አላናደደኝም፡፡ ከቤተሰቤ አባላት ማናቸውም ሊሞት የሚችልበትን እሳቤ አልቀበልም ብያለሁ፡፡ ‹‹አባቴ ጥሩ ሰው ነው ቄሱ - ምን አልባትም ካገኘኋቸው ሰዎች ሁሉ መልካሙ ሰው!››
‹‹አይ ኢማኪዩሌ አባትሽማ መጥፎ ቱትሲ ነበር - መጥፎ ሰው … የሩአግ አማጽያን የእርስ በርስ ጦርነት ያቅዱ ዘንድ ይረዳ ነበር፡፡›› ሌሎቹን ሴቶች አይተው እኔ ላይ ጠቆሙና እንዲህ አሉ፤ ‹‹ይዘው ቢገድሏችሁ በኢማኪዩሌ ምክንያት ነው፡፡ ገዳዮቹ እሷን የሚያድኗት እኮ በአባቷ ድርጊቶች ሰበብ ነው፡፡›› ቄሱ አፍጠውብኛል፤ በዚያም ላይ የሌሎቹን ሴቶች ዓይኖችም በኔ ላይ እንደ ጦር መሰካታቸው ይታወቀኛል፡፡
‹‹እናንተ ቤት ውስጥ 600 ጠመንጃዎችን አግኝተዋል›› ሲሉ ቀጠሉ ወደኔ ተመልሰው፡፡ ‹‹ቦምቦችንና የሚገደሉ ሁቱዎችን ስም ዝርዝርም አግኝተዋል፡፡ ለዚያ ነው እናንተ ቱትሲዎች እየታደናችሁና እየተገደላችሁ ያላችሁት፡፡ ሁቱዎች ቀድመው ወደ ተግባር ባይገቡ ኖሮ ይሄኔ እኛ ነበርን በቱትሲዎች የምንገደለው!›› የሚናገሩትን ለማመን አልቻልኩም፡፡ ጽንፈኛ ሁቱዎቹ የሚያሠራጯቸው መርዘኛ ውሸቶች ቄስ ሙሪንዚን ምክንያታዊነት አሳጥተዋቸዋል፡፡ ከአባቴ ጋር ለዓመታት ወዳጅ ነበሩ፡፡ አባቴ የድሆችንና ኑሮ የማይሞላላቸውን ሰዎች ሕይወት ለማሻሻል ሕይወቱን የሰጠ ሰው ነው፡፡ አባቴ ትምህርት ቤቶችንና ለቱትሲዎች፣ ለሁቱዎችና ለትዋዎች ሁሉ አነስተኛ የጸሎት ቤቶችን ሰርቷል፡፡ ታዲያ ቄሱ መሣሪያ በመደበቅም ሆነ ግድያን በማቀነባበር እንዴት ሊወነጅሉት ቻሉ? አባቴ ከደጃችን ሆነው ተስፋ የቆረጡትን ቱትሲ ስደተኞች ሁቱዎቹን ሊገድሏቸው ቢመጡ እንኳን እንዳይገድሉ አላሳሰበም ነበር?
ቄስ ሙሪንዚ ይህን መረጃቸውን ከባለሥልጣናት እንደሰሙት ነገሩኝ፡፡ ጥሎባቸው እንደ ብዙው ሩዋንዳዊ ሁሉ በሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎች የሚነግሯቸውን በጭፍን ያምናሉ፡፡
መንፈሴ ተንኮታኮተ፡፡ እንደዚህ ዓይን ያወጣ ውሸትን በአባቴ ላይ ማንም እንደዋዛ ሊያሠራጭ እንደማይችል እርግጠኛ ሆንኩ… አስቀድመው ገድለውት ካልሆነ በስተቀር፡፡ እርሱን አደገኛ ሰው አስመስሎ ማቅረብ በግልጽ የእርሱን መገደል ትክክለኛነት ለማሳየት የተጠቀሙበት እቅዳቸው መሆን አለበት፡፡ እኔ ግን ስለዚያ ላስብ አልችልም፡፡ ከቤተሰቤ ማንም ሰው ሞቷል የሚለውን ሐሳብ ለማስተናገድ አልፈለግሁም - ለዚህ ጊዜው አሁን አይደለም፡፡ ገና ያንን ለመቀበል አልጠነከርኩም፡፡ በቄሱ በጣም ስለተናደድኩባቸው ለመጮህ ፈለግሁ፤ አንዳች ነገር ማድረግ ግን እንዴት ይቻለኛል? እርሳቸው በኛና በሞት መካከል የቆሙ ብቸኛው ሰው ናቸው፡፡ ምንም እንኳን በወቅቱ ልግስናቸውን በጣም ባያሳዩንም በእርሳቸው በጎ አድራጎትና መልካም ፈቃድ ላይ ሙሉ በሙሉ ጥገኞች ነን፡፡ እኛን አደጋ ላይ እንዳለንና እገዛ እንደሚያስፈልጋቸው ጎረቤቶቻቸው ማየታቸውን እንዳቆሙ አውቀነዋል፡፡ አሁን እያዩን ያለው ልክ ገዳዮቹ አንደሚያዩን ነው - ሰው እንዳልሆንን፣ ጦርነቱ ሳያልቅ መጥፋት ዕጣ ፈንታችን እንደሆነ በረሮዎች፡፡
ቄስ ሙሪንዚ የአባቴን መልካም ስም ሲያጠፉ ንዴቴ በውስጤ ተንተገተገ፡፡ ንዴቴን መቆጣጠር አልቻልኩም - አባቴ የሚበቃውን ያህል ተዋርዷል! በመታጠቢያ ቤቱ ከቆለፉብን ወዲህ ድምጼን ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍ አደረግሁ - ‹‹አባቴ ያን ያህል መሣሪያ ቢኖረው ለምን እኛ ጋ ከለላ ፈልገው ለመጡት በሺዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች አልሰጣቸውም? ያን ያህል መሣሪያ ቢኖረው ገዳዮቹ ቤታችንን ሲያቃጥሉት ለምን አላስቆማቸውም? ሁቱዎችን ለመግደል ቢያስብ ቤተሰቡን ወደ መደበቅ ሳይገፋፉትና ኑሮውን ሳያበላሹት በገደላቸው ነበር! ይንገሩኝ ቄሱ፣ መሣሪያዎቹን ለምንድነው ሚስቱንና ሴት ልጁን ከገዳዮችና ከደፋሪዎች ለመከላከል ያልተጠቀመባቸው?››
ቄስ ሙሪንዚ ድንገት መገንፈሌ ደነገጡ (ሴቶቹም እንደዚያው - ሕይወቶቻቸውን በእጁ ከያዘው ሰው ጋር ስገዳደር ሲያዩኝ ባለማመን ዓይኖቻቸው ፈጠጡ)፡፡ ዝም እንድል በእጃቸው ተዪ የሚል ምልክት አሳዩኝ - ከዚያም መሣሪያዎች በልጅነቴ መነኩሲት እንዲያደርጉኝ ጠይቄያቸው በነበሩት በደጉ ሽማግሌ አባ ክሌሜንት ቤተክርስቲያንም እንደተገኙ ነገሩኝ፡፡ እኝህ አባት እንስሶች ሲጎዱ ማየት ስለማይፈልጉ ዕድሜ-ልካቸውን አትክልት ብቻ የሚመገቡ፣ አመፅ የሚያንገፈግፋቸውና ጠመንጃ የሚጠሉ ነበሩ፡፡ የቄሱ ሐሳብ እንዲህ ያለ ነጭ ውሸት ስለሆነ ነው መገዳደር ያለብኝ፡፡
‹‹እርስዎ ከነዚህ ከሚሏቸው መሣሪያዎች አንዱን እንኳን አይተዋል ቄሱ?›› ‹‹አይ… ግን ከትልልቅ ሰዎች ነው የሰማሁት - ከሚታመኑና ከማይዋሹ፡፡›› ከዚያን ጊዜ በፊት በተለይ በሀገሪቱ እየተከሰተ ከነበረው ነገር አንጻር የተማረ ሰው እንደዚህ እንጭጭ መሆን ይችላል ብዬ ላስብ አልችልም፡፡ ‹‹ስለዚህ አባቴን ለሚወነጅሉባቸው ነገሮች ምንም ማረጋገጫ የለዎትም፣ እስኪ ካለዎት ያምጡት፡፡›› ባዶ ነጭ ወረቀት ከኪሳቸው አውጥተው
፡
፡
#ምዕራፍ_ዘጠኝ
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የማዋየው_ወዳጅ_ሳጣ
፡
በመታጠቢያ ቤቱ ውስጥ የራሴ የምለው ስፍራ እግኝቻለሁ - የልቤን ትንሽ ጥጋት፡፡ ስነቃ ወዲያውኑ ወደዚያ አፈገፍጋለሁ፤ እስክተኛ ድረስም በዚያው እቆያለሁ፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የምነጋገርበት፣ ቃሉን የማሰላስልበትና መንፈሳዊ ማንነቴን የምንከባከብበት የተቀደሰ ስፍራዬ ነው፡፡
በምመሰጥበት ወቅት ከእምነቴ ምንጭ ደርሼ ነፍሴን አጠናክራለሁ፡፡ ሽብር ሲከበኝ በጎበኘሁት ቁጥር በሚያስደተኝና ነይ ነይ በሚለኝ ዓለም ከለላ አገኛለሁ፡፡ ሰውነቴ ሲንኮታኮት እንኳን ነፍሴ ከእግዚአብሔር ጋር ባለኝ የጠለቀ ግንኙነት ትፋፋለች::
ወደ ልዩ ስፍራዬ በጸሎት እገባለሁ፤ አንዴም ከገባሁ በኋላም ያለ ማቋረጥ እጸልያለሁ፣ መቁጠሪያዬን ሃሳቤንና ሃይሌን ወደ እግዚአብሔር እንዳተኩር እንደመልህቅ እጠቀመዋለሁ፡፡ የመቁጠሪያው ዶቃዎች በወንጌል ላይ እንዳተኩርና የእግዚአብሔርን ቃል በአእምሮዬ ህያው አድርጌ እንዳቆይ ረድተውኛል፡፡ በጸጥታ እጸልያለሁ፤ ግን ራሴን በእውነት እያልኳቸው እንደሆነ ለማሳመን ሁልጊዜ ቃላቱን በአፌ ድምፅ ሳላሰማ እላቸዋለሁ… ያ ባይሆን ኖሮ ጥርጣሬ ይገባኝና አሉታዊው ኃይል እየተጣራ ይመጣብኛል፡፡
የአንድን ነጠላ ቃል ትርጉም ሳሰላስል ሰዓታትን እወስዳለሁ፣ እንደ ምኅረት፣ እምነት ወይም ተስፋ ያሉትን፡፡ እጅ መስጠት የሚለውን ቃል ሳሰላስል ቀናትን አሳልፌያለሁ፡፡ በዚህም ምክንያት የራስን ስብዕና ለአንድ ከፍ ላለ ኃይል መስጠት ማለት ምን ማለት እንደሆነ ተረዳሁ፡፡ ራሴን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር አሳልፌ ሰጠሁ፡፡ በማልጸልይበት ጊዜ በእርሱ ብርሃን ውስጥ እንዳልሆንኩ ይሰማኛል፤ የመታጠቢያ ክፍሉ ዓለምም በበኩሉ ለመቋቋም የሚከብድ ነው፡፡ በተደበቅንበት የመጀመሪያው ወር መጨረሻ አካባቢ ቄስ ሙሪንዚ አንድ ሌሊት ላይ በጣም አምሽተው ትርፍራፊ ምግብ ይዘውልን መጡ፡፡ ወደዚህ ሲያስገቡን በሃዘኔታ ስሜት ቢሆንም አሁን ግን ያ እየጠፋ የሄደ መሰለ፡፡ በዚህ ምሽት ፊታቸው ከወትሮው የአሳቢነትና የሃዘኔታ ገጽታ ወደ መኮሳተር መጣ፡፡ ‹‹አባትሽ በጣም መጥፎ ቱትሲ ነበር!›› ሲሉ አያገጣብሩኝም!
‹‹ምን? ምን ማለትዎ ነው?›› ሙሉ በሙሉ የማደርገውን አሳጣኝ፤ ቢሆንም ግን በአባቴ ላይ የሰነዘሩት ጥቃት አባቴን ባለፈ ጊዜ የመግለጻቸውን ያህል አላናደደኝም፡፡ ከቤተሰቤ አባላት ማናቸውም ሊሞት የሚችልበትን እሳቤ አልቀበልም ብያለሁ፡፡ ‹‹አባቴ ጥሩ ሰው ነው ቄሱ - ምን አልባትም ካገኘኋቸው ሰዎች ሁሉ መልካሙ ሰው!››
‹‹አይ ኢማኪዩሌ አባትሽማ መጥፎ ቱትሲ ነበር - መጥፎ ሰው … የሩአግ አማጽያን የእርስ በርስ ጦርነት ያቅዱ ዘንድ ይረዳ ነበር፡፡›› ሌሎቹን ሴቶች አይተው እኔ ላይ ጠቆሙና እንዲህ አሉ፤ ‹‹ይዘው ቢገድሏችሁ በኢማኪዩሌ ምክንያት ነው፡፡ ገዳዮቹ እሷን የሚያድኗት እኮ በአባቷ ድርጊቶች ሰበብ ነው፡፡›› ቄሱ አፍጠውብኛል፤ በዚያም ላይ የሌሎቹን ሴቶች ዓይኖችም በኔ ላይ እንደ ጦር መሰካታቸው ይታወቀኛል፡፡
‹‹እናንተ ቤት ውስጥ 600 ጠመንጃዎችን አግኝተዋል›› ሲሉ ቀጠሉ ወደኔ ተመልሰው፡፡ ‹‹ቦምቦችንና የሚገደሉ ሁቱዎችን ስም ዝርዝርም አግኝተዋል፡፡ ለዚያ ነው እናንተ ቱትሲዎች እየታደናችሁና እየተገደላችሁ ያላችሁት፡፡ ሁቱዎች ቀድመው ወደ ተግባር ባይገቡ ኖሮ ይሄኔ እኛ ነበርን በቱትሲዎች የምንገደለው!›› የሚናገሩትን ለማመን አልቻልኩም፡፡ ጽንፈኛ ሁቱዎቹ የሚያሠራጯቸው መርዘኛ ውሸቶች ቄስ ሙሪንዚን ምክንያታዊነት አሳጥተዋቸዋል፡፡ ከአባቴ ጋር ለዓመታት ወዳጅ ነበሩ፡፡ አባቴ የድሆችንና ኑሮ የማይሞላላቸውን ሰዎች ሕይወት ለማሻሻል ሕይወቱን የሰጠ ሰው ነው፡፡ አባቴ ትምህርት ቤቶችንና ለቱትሲዎች፣ ለሁቱዎችና ለትዋዎች ሁሉ አነስተኛ የጸሎት ቤቶችን ሰርቷል፡፡ ታዲያ ቄሱ መሣሪያ በመደበቅም ሆነ ግድያን በማቀነባበር እንዴት ሊወነጅሉት ቻሉ? አባቴ ከደጃችን ሆነው ተስፋ የቆረጡትን ቱትሲ ስደተኞች ሁቱዎቹን ሊገድሏቸው ቢመጡ እንኳን እንዳይገድሉ አላሳሰበም ነበር?
ቄስ ሙሪንዚ ይህን መረጃቸውን ከባለሥልጣናት እንደሰሙት ነገሩኝ፡፡ ጥሎባቸው እንደ ብዙው ሩዋንዳዊ ሁሉ በሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎች የሚነግሯቸውን በጭፍን ያምናሉ፡፡
መንፈሴ ተንኮታኮተ፡፡ እንደዚህ ዓይን ያወጣ ውሸትን በአባቴ ላይ ማንም እንደዋዛ ሊያሠራጭ እንደማይችል እርግጠኛ ሆንኩ… አስቀድመው ገድለውት ካልሆነ በስተቀር፡፡ እርሱን አደገኛ ሰው አስመስሎ ማቅረብ በግልጽ የእርሱን መገደል ትክክለኛነት ለማሳየት የተጠቀሙበት እቅዳቸው መሆን አለበት፡፡ እኔ ግን ስለዚያ ላስብ አልችልም፡፡ ከቤተሰቤ ማንም ሰው ሞቷል የሚለውን ሐሳብ ለማስተናገድ አልፈለግሁም - ለዚህ ጊዜው አሁን አይደለም፡፡ ገና ያንን ለመቀበል አልጠነከርኩም፡፡ በቄሱ በጣም ስለተናደድኩባቸው ለመጮህ ፈለግሁ፤ አንዳች ነገር ማድረግ ግን እንዴት ይቻለኛል? እርሳቸው በኛና በሞት መካከል የቆሙ ብቸኛው ሰው ናቸው፡፡ ምንም እንኳን በወቅቱ ልግስናቸውን በጣም ባያሳዩንም በእርሳቸው በጎ አድራጎትና መልካም ፈቃድ ላይ ሙሉ በሙሉ ጥገኞች ነን፡፡ እኛን አደጋ ላይ እንዳለንና እገዛ እንደሚያስፈልጋቸው ጎረቤቶቻቸው ማየታቸውን እንዳቆሙ አውቀነዋል፡፡ አሁን እያዩን ያለው ልክ ገዳዮቹ አንደሚያዩን ነው - ሰው እንዳልሆንን፣ ጦርነቱ ሳያልቅ መጥፋት ዕጣ ፈንታችን እንደሆነ በረሮዎች፡፡
ቄስ ሙሪንዚ የአባቴን መልካም ስም ሲያጠፉ ንዴቴ በውስጤ ተንተገተገ፡፡ ንዴቴን መቆጣጠር አልቻልኩም - አባቴ የሚበቃውን ያህል ተዋርዷል! በመታጠቢያ ቤቱ ከቆለፉብን ወዲህ ድምጼን ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍ አደረግሁ - ‹‹አባቴ ያን ያህል መሣሪያ ቢኖረው ለምን እኛ ጋ ከለላ ፈልገው ለመጡት በሺዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች አልሰጣቸውም? ያን ያህል መሣሪያ ቢኖረው ገዳዮቹ ቤታችንን ሲያቃጥሉት ለምን አላስቆማቸውም? ሁቱዎችን ለመግደል ቢያስብ ቤተሰቡን ወደ መደበቅ ሳይገፋፉትና ኑሮውን ሳያበላሹት በገደላቸው ነበር! ይንገሩኝ ቄሱ፣ መሣሪያዎቹን ለምንድነው ሚስቱንና ሴት ልጁን ከገዳዮችና ከደፋሪዎች ለመከላከል ያልተጠቀመባቸው?››
ቄስ ሙሪንዚ ድንገት መገንፈሌ ደነገጡ (ሴቶቹም እንደዚያው - ሕይወቶቻቸውን በእጁ ከያዘው ሰው ጋር ስገዳደር ሲያዩኝ ባለማመን ዓይኖቻቸው ፈጠጡ)፡፡ ዝም እንድል በእጃቸው ተዪ የሚል ምልክት አሳዩኝ - ከዚያም መሣሪያዎች በልጅነቴ መነኩሲት እንዲያደርጉኝ ጠይቄያቸው በነበሩት በደጉ ሽማግሌ አባ ክሌሜንት ቤተክርስቲያንም እንደተገኙ ነገሩኝ፡፡ እኝህ አባት እንስሶች ሲጎዱ ማየት ስለማይፈልጉ ዕድሜ-ልካቸውን አትክልት ብቻ የሚመገቡ፣ አመፅ የሚያንገፈግፋቸውና ጠመንጃ የሚጠሉ ነበሩ፡፡ የቄሱ ሐሳብ እንዲህ ያለ ነጭ ውሸት ስለሆነ ነው መገዳደር ያለብኝ፡፡
‹‹እርስዎ ከነዚህ ከሚሏቸው መሣሪያዎች አንዱን እንኳን አይተዋል ቄሱ?›› ‹‹አይ… ግን ከትልልቅ ሰዎች ነው የሰማሁት - ከሚታመኑና ከማይዋሹ፡፡›› ከዚያን ጊዜ በፊት በተለይ በሀገሪቱ እየተከሰተ ከነበረው ነገር አንጻር የተማረ ሰው እንደዚህ እንጭጭ መሆን ይችላል ብዬ ላስብ አልችልም፡፡ ‹‹ስለዚህ አባቴን ለሚወነጅሉባቸው ነገሮች ምንም ማረጋገጫ የለዎትም፣ እስኪ ካለዎት ያምጡት፡፡›› ባዶ ነጭ ወረቀት ከኪሳቸው አውጥተው
👍2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስር
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#በልሳን_ሲያናግረኝ
፡
፡
በመታጠቢያ ቤቱ ሰባት ሳምንታት መቆየታችን ሁላችንንም በሚያስደነግጥ ሁኔታ አክስቶናል — አጥንቶቻችን ገጠው ወጥተዋል፤ ቆዳችንም አሸበሸበ፡፡ በሰውነታችን ውስጥ የነበረው ስብና ጡንቻዎቻችን ጠፍተው፣ መቀመጫችንም አጥንቱ ብቻ ስለቀረ በጠጣሩ ወለል ላይ መቀመጡ አልስማማ ይለን ጀመር፡፡ ሁለት ሴቶች ቢጨመሩብንም መታጠቢያ ቤቱ ግን ከቀን ወደ ቀን እየሰፋ ሄደ፡፡ መነመንን፤ ተቆጥቦ የሚሰጠን ምግብም ብዙውን ጊዜ ያደካክመንና ራሳችንንም ያዞረን ገባ፡፡ በልብሶቼ መስፋት ቢያንስ 17 ኪሎግራም እንደቀነስኩ መናገር እችላለሁ (መጀመሪያ ላይ ወደ
50 ኪሎግራም እመዝን ነበር)፡፡
ቆዳችን ቀልቶ፣ ከንፈሮቻችን ተሰነጣጥቀው፣ ድዶቻችንም አባብጠውና ቆሳስለው እጅግ ተጎድተናል፡፡ በዚያ ላይ ከደረስንበት ጊዜ ጀምሮ ታጥበንም ሆነ ልብስ ቀይረን ስለማናውቅ በአሰቃቂ የተባይ ወረራ ተቸገርን፡፡ አንዳንዴ ትናንሾቹ ተባዮች ደማችንን መጠው ስለሚያብጡ በፊታችን ላይ ሲንፈላሰሱ እናያቸዋለን፡፡ ሲያዩን የምናማልል ላንሆን እንችላለን፡፡ ግን ከዚያ በላይ ቆንጆነት ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ በየቀኑ እነሳና እግዚአብሔርን ሕይወትን ስለሰጠኝ አመሰግነዋለሁ፡፡ አምላኬም በየጠዋቱ እንደምወደድና የብርቅዮ እንደምያዝ እንዲሰማኝ አደረገኝ፡፡ ይህን ያህል ጊዜ በሕይወት ያቆየኝና በብዙ ሥቃይ ውስጥ ያሳለፈኝ በደም በሰከረ ገዳይ ገጀራ እንድገደል እንዳልሆነ አውቃለሁ! በአንድ የማይረባ የዕለት ህመም እንድሞት እንደማያደርገኝም ይታወቀኛል፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ ለሁለት ጊዜ ያክል በተወሰኑ ክኒኖች በአንድ ቀን ልቆጣጠራቸው በምችላቸው ህመሞች ተይዤ ነበር … ኪኒን ቢኖረን ኖሮ፡፡ የመጀመሪያው ህመሜ በመንዘፍዘፍና በራስ ምታት ባሰቃየኝ በ40.5 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት ታጅቦ ነበር የመጣው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ አሳልፌ ከማውቃቸው በጣም አሰቃቂ ክስተቶች አንዱ የሆነው አስከፊ የሽንት ቧንቧ መመረዝ ነበር፡፡ ቄሱ ሊያቀርቡልኝ የቻሉት ብቸኛው ነገር የሙቀት መለኪያ መሣሪያና መልካም ምኞታቸውን ነበር - የቀረ ምንም መድኃኒት አልነበራቸውም፡፡
ማድረግ የምችለው ብቸኛው ነገር መጸለይ በመሆኑ ያንን ብቻ ነበር ያደረግሁት፡፡ ሕመሙና ትኩሳቱ ከምችለው በላይ ሲሆንብኝ አምላክ እንደተኛሁ ፈዋሽ እጆቹን እንዲያሣርፍብኝ ጠየቅሁት፡፡ በሁለቱም ጊዜያት ያለምንም ትኩሳትና ህመም
ተነቃቅቼና ደኅና ሆኜ ተነሣሁ፡፡ በፍቅሩ ኃይል ተፈወስኩ፡፡
ምንም ዓይነት ህመም ሕይወቴን እንደማይነጥቀኝ ተማምኛለሁ፡፡ አምላክ ለእኔ አንድ ታላቅ ዓላማ እንደነበረው እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ እናም በየቀኑ ያንን ይገልጽልኝ ዘንድ እጠይቀዋለሁ፡፡ መጀመሪያ ላይማ ሁሉንም የወደፊት ሕይወቴን ባንዴ እንዲያሳየኝ እጠብቃለሁ፡፡ ምናልባት ለጥሩ ዓላማ እንደተሰነዘሩ ሁሉ፤ ልክ እንደ መብረቅ ብልጭታና እንደ ድርቅርቅ ምች፡፡ ግን አምላክ ምንም ቢሆን አንድን ልንረዳው ያልተዘጋጀንለት ነገር እንድናይ እንደማያደርገን እየተማርኩ መጣሁ፡፡ ይልቁኑ ለማየት የሚያስፈልገንን ልናይ በሚገባን ጊዜ እንድናይ ያደርገናል፡፡ ዓይናችንና ልባችን ክፍት እስኪሆኑለትም ይጠብቃል፡፡ ዝግጁም ሲሆኑ እግሮቻችንን ለኛ አመቺ በሆነው መንገድ ላይ ያስቀምጣቸዋል…. መራመዱ ግን የኛ ድርሻ ይሆናል፡፡
ቄስ ሙሪንዚ አንድ ቀን ስለ ጦርነቱ ሲያወሩ ጌታ ትክክለኛውን ነገር አስመለከተኝ፡፡ የተመድ የሰላም አስከባሪ ወታደሮቹን ወደ ሩዋንዳ ሊልክ ስላቀደ ለጦርነቱ ፍጻሜ ያበጅለታል ብለው በማሰብ ቄሱ በጣም ተደሰቱ፡፡ የተመድ አሥር ቤልጅዬማውያን ሰላም አስከባሪዎች በዘር ፍጅቱ የመጀመሪያ ቀን በሁቱ ወታደሮች ከተገደሉበት በኋላ አብዛኞቹን ወታደሮቹን አስወጥቷል፡፡ በእርግጥ ሁሉም ምዕራባዊ ሀገር ቱትሲዎችን ዕጣ ፈንታቸውን ብቻቸውን ይጋፈጧት ዘንድ በመተው ዜጎቹን ከሀገሪቱ አስወጥቷል፡፡ የዘር ፍጅቱ ከጀመረ ወዲህ ምንም የውጪ ዜጎች አልነበሩም ማለት ይቻላል - ያም ለኛ መንግሥት የዘር ፍጅትም ቢያካሂድ ዓለም ግድ እንደማይሰጠውና የቱትሲዎች ሕይወት ዋጋ እንደሌለው መልዕክት አስተላልፎለታል፡፡ ስለሆነም ግድያው ቀጠለ፡፡
የተመድ አዲስ ጦር መላኩ ትልቅ ነገር ነው… የዘር ፍጅቱን ሳይቀር ሊያስቆመው ይችላል! ቄሱ ግን ችግር እንዳለ ይናገራሉ፡፡ ‹‹በሩአግ ውስጥ ያሉት ቱትሲዎች የተመድ ወታደሮቹን እንዲልክ አይፈልጉም፡፡ ምክንያቱም ጦርነቱ እንዲቀጥል ስለሚፈልጉ ነው፡፡ ጦርነቱን እንደሚያሸንፉና ሥልጣን እንደሚይዙ ያስባሉ!›› ሲሉ ጮሁብን፡፡ ‹‹ወግ ወጉ ተይዞልኛል፡፡ የተመድ ወታደሮችን ከላከ እንግሊዝኛ ተናጋሪ መሆን እንዳለባቸው እየጠየቁ ነው … ይህን ያህል ድፍረት!››
ቄሱ አብዛኞቹ የሩአግ ወታደሮች በብሪታንያ ቅኝ በተገዛችው በዩጋንዳ ያደጉ ስለሆኑ እንግሊዝኛ እንደሚናገሩ ነገሩን፡፡ ይህም ፈረንሳይኛ በሚነገርባት በቤልጅዬም ከተገዛችው ከሩዋንዳ ጋር ይቃረናል፡፡ አብዛኞቻችን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፈረንሳይኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋችን ተምረናል፡፡
‹‹የራሱ ወታደሮች ፈረንሳይኛ ቢችሉም እንኳን ሩአግ አንናገርም ብሎ ይቃወማል›› ቄስ ሙሪንዚ ጨመሩልን፡፡ ‹‹የፈረንሳይ ጦር ሠራዊት የኢንተርሃምዌን ገዳዮች አሰልጥኗል ብለው ይወነጅላሉ፡፡ ፈረንሳውያንን ይጠሏቸዋል… ሩአግ ጦርነቱን የሚያሸንፍ ከሆነ ሁላችንንም እንግሊዝኛ እንድንናገር ያደርጉናል!›› አምላክ በአእምሮዬ አንዳች ብርሃን አበራልኝ፡፡
ሁሉም ነገር የሆነው በቅጽበት ነው፡፡ በዚያን አፍታ ሩአግ ጦርነቱን እንደሚያሸንፍ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ይህም ማለት እኔ እንግሊዝኛ ተናጋሪ የሆኑ ሰዎችን ከዘር ፍጅቱ በኋላ አገኝና የደረሰብንን ሁሉ የተከሰተውን እነግራቸዋለሁ ማለት ነው፡፡ ሀሉም ሰው እንግሊዝኛ ብቻ በሚናገርበት በተመድ ውስጥ እንደምሠራም ራእይ ታየኝ፡፡ ድንገት በመታጠቢያ ቤቱ ውስጥ ያለውን ቀሪውን ጊዜዬን እንግሊዝኛ ቋንቋን ስናገር አንደማሳልፍ በግልጽ ታወቀኝ፡፡ አምላክ የአንድን ትልቅ ሕጋዊ ቁማር አሸናፊ ቁጥሮች እንደሰጠኝ ተሰማኝ… ማድረግ የነበረብኝ ብቸኛው ነገር ቢኖር ዕጣው ሲወጣ ዝግጁ መሆኔን ማረጋገጥ ይሆናል፡፡ ዕጣ ፈንታዬን ለመጋፈጥ መዘጋጀት ነበረብኝ!
ፍጹም እንግዳ የሆነን ቋንቋ መማር የብዙ ሰዓታት ጥናት እንደሚጠይቅ አውቃለሁ፤ ይህም ጸሎቴን እንድቀንስ ያስገድደኛል፡፡ ይህም መሆኑ ለዲያብሎስ የሚጠብቀውን ዕድል ይሰጠዋል ብዬ ሠጋሁ፡፡ ወደ አእምሮዬ ተመልሶ ዘሎ ገብቶ በፍርሃትና በጥርጣሬ ሞልቶኝ ወደ ጨለማና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይከተኛል፡፡ ማድረግ የምችለውን ብቸኛውን ነገር አደረግሁ፡፡ አምላክን ምን እንደማደርግ ጠየኩት፡፡ ውድ እግዚአብሔር - ይህን እንግሊዝኛ ተማሪ የሚለውን ሐሳብ አንተ ወደ ራሴ ከተኸዋል፤ ስለዚህ በማጠናበት ጊዜ ዲያብሎስን አርቅልኝ! እባክህ እዚህ መታጠቢያ ቤት ውስጥ ተቀርቅሬ አዲስ ቋንቋ እንዴት አንደምማር አሳየኝ፡፡ ለሌሎቹ ሴቶች ስለ ዕቅዴ ለመንገር ግድም አልሰጠኝ - በዚያ በምጸልይበት መንገድ ስጸልይ ሲያዩ ነገሩን ቀለል አድርጌ እንዳየሁት አስበዋል፡፡ ሕይወታችንን ለማትረፍ ስንጣጣር የውጪ ቋንቋ ለመቻል እንደፈለግሁ ብነግራቸው ቄሱን ለአንድ አባሺ ጎሳ አባል ወዲያውኑ አሳልፈው እንዲሰጡኝ ሊጠይቋቸው ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ህልሞቼን ለራሴ ይዤ ቆየሁ፡፡
፡
፡
#ምዕራፍ_አስር
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#በልሳን_ሲያናግረኝ
፡
፡
በመታጠቢያ ቤቱ ሰባት ሳምንታት መቆየታችን ሁላችንንም በሚያስደነግጥ ሁኔታ አክስቶናል — አጥንቶቻችን ገጠው ወጥተዋል፤ ቆዳችንም አሸበሸበ፡፡ በሰውነታችን ውስጥ የነበረው ስብና ጡንቻዎቻችን ጠፍተው፣ መቀመጫችንም አጥንቱ ብቻ ስለቀረ በጠጣሩ ወለል ላይ መቀመጡ አልስማማ ይለን ጀመር፡፡ ሁለት ሴቶች ቢጨመሩብንም መታጠቢያ ቤቱ ግን ከቀን ወደ ቀን እየሰፋ ሄደ፡፡ መነመንን፤ ተቆጥቦ የሚሰጠን ምግብም ብዙውን ጊዜ ያደካክመንና ራሳችንንም ያዞረን ገባ፡፡ በልብሶቼ መስፋት ቢያንስ 17 ኪሎግራም እንደቀነስኩ መናገር እችላለሁ (መጀመሪያ ላይ ወደ
50 ኪሎግራም እመዝን ነበር)፡፡
ቆዳችን ቀልቶ፣ ከንፈሮቻችን ተሰነጣጥቀው፣ ድዶቻችንም አባብጠውና ቆሳስለው እጅግ ተጎድተናል፡፡ በዚያ ላይ ከደረስንበት ጊዜ ጀምሮ ታጥበንም ሆነ ልብስ ቀይረን ስለማናውቅ በአሰቃቂ የተባይ ወረራ ተቸገርን፡፡ አንዳንዴ ትናንሾቹ ተባዮች ደማችንን መጠው ስለሚያብጡ በፊታችን ላይ ሲንፈላሰሱ እናያቸዋለን፡፡ ሲያዩን የምናማልል ላንሆን እንችላለን፡፡ ግን ከዚያ በላይ ቆንጆነት ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ በየቀኑ እነሳና እግዚአብሔርን ሕይወትን ስለሰጠኝ አመሰግነዋለሁ፡፡ አምላኬም በየጠዋቱ እንደምወደድና የብርቅዮ እንደምያዝ እንዲሰማኝ አደረገኝ፡፡ ይህን ያህል ጊዜ በሕይወት ያቆየኝና በብዙ ሥቃይ ውስጥ ያሳለፈኝ በደም በሰከረ ገዳይ ገጀራ እንድገደል እንዳልሆነ አውቃለሁ! በአንድ የማይረባ የዕለት ህመም እንድሞት እንደማያደርገኝም ይታወቀኛል፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ ለሁለት ጊዜ ያክል በተወሰኑ ክኒኖች በአንድ ቀን ልቆጣጠራቸው በምችላቸው ህመሞች ተይዤ ነበር … ኪኒን ቢኖረን ኖሮ፡፡ የመጀመሪያው ህመሜ በመንዘፍዘፍና በራስ ምታት ባሰቃየኝ በ40.5 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት ታጅቦ ነበር የመጣው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ አሳልፌ ከማውቃቸው በጣም አሰቃቂ ክስተቶች አንዱ የሆነው አስከፊ የሽንት ቧንቧ መመረዝ ነበር፡፡ ቄሱ ሊያቀርቡልኝ የቻሉት ብቸኛው ነገር የሙቀት መለኪያ መሣሪያና መልካም ምኞታቸውን ነበር - የቀረ ምንም መድኃኒት አልነበራቸውም፡፡
ማድረግ የምችለው ብቸኛው ነገር መጸለይ በመሆኑ ያንን ብቻ ነበር ያደረግሁት፡፡ ሕመሙና ትኩሳቱ ከምችለው በላይ ሲሆንብኝ አምላክ እንደተኛሁ ፈዋሽ እጆቹን እንዲያሣርፍብኝ ጠየቅሁት፡፡ በሁለቱም ጊዜያት ያለምንም ትኩሳትና ህመም
ተነቃቅቼና ደኅና ሆኜ ተነሣሁ፡፡ በፍቅሩ ኃይል ተፈወስኩ፡፡
ምንም ዓይነት ህመም ሕይወቴን እንደማይነጥቀኝ ተማምኛለሁ፡፡ አምላክ ለእኔ አንድ ታላቅ ዓላማ እንደነበረው እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ እናም በየቀኑ ያንን ይገልጽልኝ ዘንድ እጠይቀዋለሁ፡፡ መጀመሪያ ላይማ ሁሉንም የወደፊት ሕይወቴን ባንዴ እንዲያሳየኝ እጠብቃለሁ፡፡ ምናልባት ለጥሩ ዓላማ እንደተሰነዘሩ ሁሉ፤ ልክ እንደ መብረቅ ብልጭታና እንደ ድርቅርቅ ምች፡፡ ግን አምላክ ምንም ቢሆን አንድን ልንረዳው ያልተዘጋጀንለት ነገር እንድናይ እንደማያደርገን እየተማርኩ መጣሁ፡፡ ይልቁኑ ለማየት የሚያስፈልገንን ልናይ በሚገባን ጊዜ እንድናይ ያደርገናል፡፡ ዓይናችንና ልባችን ክፍት እስኪሆኑለትም ይጠብቃል፡፡ ዝግጁም ሲሆኑ እግሮቻችንን ለኛ አመቺ በሆነው መንገድ ላይ ያስቀምጣቸዋል…. መራመዱ ግን የኛ ድርሻ ይሆናል፡፡
ቄስ ሙሪንዚ አንድ ቀን ስለ ጦርነቱ ሲያወሩ ጌታ ትክክለኛውን ነገር አስመለከተኝ፡፡ የተመድ የሰላም አስከባሪ ወታደሮቹን ወደ ሩዋንዳ ሊልክ ስላቀደ ለጦርነቱ ፍጻሜ ያበጅለታል ብለው በማሰብ ቄሱ በጣም ተደሰቱ፡፡ የተመድ አሥር ቤልጅዬማውያን ሰላም አስከባሪዎች በዘር ፍጅቱ የመጀመሪያ ቀን በሁቱ ወታደሮች ከተገደሉበት በኋላ አብዛኞቹን ወታደሮቹን አስወጥቷል፡፡ በእርግጥ ሁሉም ምዕራባዊ ሀገር ቱትሲዎችን ዕጣ ፈንታቸውን ብቻቸውን ይጋፈጧት ዘንድ በመተው ዜጎቹን ከሀገሪቱ አስወጥቷል፡፡ የዘር ፍጅቱ ከጀመረ ወዲህ ምንም የውጪ ዜጎች አልነበሩም ማለት ይቻላል - ያም ለኛ መንግሥት የዘር ፍጅትም ቢያካሂድ ዓለም ግድ እንደማይሰጠውና የቱትሲዎች ሕይወት ዋጋ እንደሌለው መልዕክት አስተላልፎለታል፡፡ ስለሆነም ግድያው ቀጠለ፡፡
የተመድ አዲስ ጦር መላኩ ትልቅ ነገር ነው… የዘር ፍጅቱን ሳይቀር ሊያስቆመው ይችላል! ቄሱ ግን ችግር እንዳለ ይናገራሉ፡፡ ‹‹በሩአግ ውስጥ ያሉት ቱትሲዎች የተመድ ወታደሮቹን እንዲልክ አይፈልጉም፡፡ ምክንያቱም ጦርነቱ እንዲቀጥል ስለሚፈልጉ ነው፡፡ ጦርነቱን እንደሚያሸንፉና ሥልጣን እንደሚይዙ ያስባሉ!›› ሲሉ ጮሁብን፡፡ ‹‹ወግ ወጉ ተይዞልኛል፡፡ የተመድ ወታደሮችን ከላከ እንግሊዝኛ ተናጋሪ መሆን እንዳለባቸው እየጠየቁ ነው … ይህን ያህል ድፍረት!››
ቄሱ አብዛኞቹ የሩአግ ወታደሮች በብሪታንያ ቅኝ በተገዛችው በዩጋንዳ ያደጉ ስለሆኑ እንግሊዝኛ እንደሚናገሩ ነገሩን፡፡ ይህም ፈረንሳይኛ በሚነገርባት በቤልጅዬም ከተገዛችው ከሩዋንዳ ጋር ይቃረናል፡፡ አብዛኞቻችን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፈረንሳይኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋችን ተምረናል፡፡
‹‹የራሱ ወታደሮች ፈረንሳይኛ ቢችሉም እንኳን ሩአግ አንናገርም ብሎ ይቃወማል›› ቄስ ሙሪንዚ ጨመሩልን፡፡ ‹‹የፈረንሳይ ጦር ሠራዊት የኢንተርሃምዌን ገዳዮች አሰልጥኗል ብለው ይወነጅላሉ፡፡ ፈረንሳውያንን ይጠሏቸዋል… ሩአግ ጦርነቱን የሚያሸንፍ ከሆነ ሁላችንንም እንግሊዝኛ እንድንናገር ያደርጉናል!›› አምላክ በአእምሮዬ አንዳች ብርሃን አበራልኝ፡፡
ሁሉም ነገር የሆነው በቅጽበት ነው፡፡ በዚያን አፍታ ሩአግ ጦርነቱን እንደሚያሸንፍ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ይህም ማለት እኔ እንግሊዝኛ ተናጋሪ የሆኑ ሰዎችን ከዘር ፍጅቱ በኋላ አገኝና የደረሰብንን ሁሉ የተከሰተውን እነግራቸዋለሁ ማለት ነው፡፡ ሀሉም ሰው እንግሊዝኛ ብቻ በሚናገርበት በተመድ ውስጥ እንደምሠራም ራእይ ታየኝ፡፡ ድንገት በመታጠቢያ ቤቱ ውስጥ ያለውን ቀሪውን ጊዜዬን እንግሊዝኛ ቋንቋን ስናገር አንደማሳልፍ በግልጽ ታወቀኝ፡፡ አምላክ የአንድን ትልቅ ሕጋዊ ቁማር አሸናፊ ቁጥሮች እንደሰጠኝ ተሰማኝ… ማድረግ የነበረብኝ ብቸኛው ነገር ቢኖር ዕጣው ሲወጣ ዝግጁ መሆኔን ማረጋገጥ ይሆናል፡፡ ዕጣ ፈንታዬን ለመጋፈጥ መዘጋጀት ነበረብኝ!
ፍጹም እንግዳ የሆነን ቋንቋ መማር የብዙ ሰዓታት ጥናት እንደሚጠይቅ አውቃለሁ፤ ይህም ጸሎቴን እንድቀንስ ያስገድደኛል፡፡ ይህም መሆኑ ለዲያብሎስ የሚጠብቀውን ዕድል ይሰጠዋል ብዬ ሠጋሁ፡፡ ወደ አእምሮዬ ተመልሶ ዘሎ ገብቶ በፍርሃትና በጥርጣሬ ሞልቶኝ ወደ ጨለማና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይከተኛል፡፡ ማድረግ የምችለውን ብቸኛውን ነገር አደረግሁ፡፡ አምላክን ምን እንደማደርግ ጠየኩት፡፡ ውድ እግዚአብሔር - ይህን እንግሊዝኛ ተማሪ የሚለውን ሐሳብ አንተ ወደ ራሴ ከተኸዋል፤ ስለዚህ በማጠናበት ጊዜ ዲያብሎስን አርቅልኝ! እባክህ እዚህ መታጠቢያ ቤት ውስጥ ተቀርቅሬ አዲስ ቋንቋ እንዴት አንደምማር አሳየኝ፡፡ ለሌሎቹ ሴቶች ስለ ዕቅዴ ለመንገር ግድም አልሰጠኝ - በዚያ በምጸልይበት መንገድ ስጸልይ ሲያዩ ነገሩን ቀለል አድርጌ እንዳየሁት አስበዋል፡፡ ሕይወታችንን ለማትረፍ ስንጣጣር የውጪ ቋንቋ ለመቻል እንደፈለግሁ ብነግራቸው ቄሱን ለአንድ አባሺ ጎሳ አባል ወዲያውኑ አሳልፈው እንዲሰጡኝ ሊጠይቋቸው ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ህልሞቼን ለራሴ ይዤ ቆየሁ፡፡
👍1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምእራፍ_አስራ_አንድ
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#እምነቴን_ስጠብቅ
፡
፡
ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰምቻቸዋለሁ፡፡
የፍርሃት መአት በውስጤ ተሠራጨ፡፡ ዲያብሎስም ድጋሚ በጆሮዬ አንሾካሾከ - አሁን የት እንዳለሽ አውቀውታል… አሁን የት እንዳለሽ አውቀውታል… አእምሮዬ ወደ ድሮው ተመለሰና ራሴን ሳትኩ፡፡ ለምን ስሜን ተጣሩ - እዚህ እንዳለሁ እንዴት ሊያውቁ ቻሉ? ወደ መታጠቢያ ቤቱ እየመጡ ይሆን እንዴ?
አምላክን ለመጥራት ብሞክርም የምሰማው ብቸኛ ነገር ግን በቤቱ ከሚያስተጋቡት ከገዳዮቹ ክፉና አረመኔያዊ መዝሙሮች ጋር አእምሮዬን የተቆጣጠሩትን አሉታዊ ድምጾች ነው፡፡ ልብሶቼ በላብ ተጠምቀው እምነቴን ፍለጋ እፍጨረጨር ገባሁ፡፡
የመጡት በመቶዎች ሆነው ነው፡፡ ቄሱን የዛቻና የውንጀላ መዓት ያወርዱባቸዋል፡፡ ‹‹የት ነች?›› ሲሉ አንባረቁባቸው፡፡ ‹‹እዚህ እንዳለች እናውቃለን፡፡ ፈልጓት… ኢማኪዩሌን ፈልጓት፡፡››
ከግንቡ በስተጀርባ በቄሱ መኝታ ቤት ናቸው፡፡ ከግማሽ ጋት ያነሰ ውፍረት ያለው ጭቃና ዕንጨት ይለያየናል፡፡ እርምጃዎቻቸው ቤቱን አንቀጠቀጡት፣ ገጀራዎቻቸውና ጦሮቻቸውም ከግንቡ ጋር ሲጋጩ ይሰማኛል፡፡
በረብሻው መካከል አንድ የቤተሰቤ ወዳጅ የሆነን ሰው ድምፅ መለየት ቻልኩ፡፡ ‹‹399 በረሮዎችን ገድያለሁ›› በማለት ጉራውን ይነፋል፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ 400 ታደርግልኛለች፡፡ ይህም ቀላል የሚባል ቁጥር አይደለም፡፡››
በጥጋቷ እንደተሸሸግሁ ዲያብሎስ በጆሮዬ ይስቅብኛል፡፡ ስምሽን ያውቃሉ… እዚህ እንዳለሽ ያውቃሉ፡፡ አሁንስ አምላክሽ የት አለ?
ገዳዮቹ ቄሱን ተጫኗቸው፡- ‹‹ቱትሲዎቹ የት ናቸው? ካገኘናቸው ምን እንደምናደርጋቸው ታውቃለህ፡፡ የት አለች፤ ቄሱ፣ ኢማኪዩሌ የት ነች? መጨረሻ የታየችበት ስፍራ እዚህ ነው፡፡ የት ነው የደበቅሃት?››
መንፈሴ በፍርሃትና ጥርጣሬ ክንዶች ላይ ተመልሶ ወደቀ፡፡ እናም ገዳዮቹ መጀመሪያ በመጡበት ጊዜ ከፈራሁትም በላይ በጣም ፈራሁ፡፡ ድምጾቻቸው ሥጋዬን ሸነታተሩት፤ በመቀጣጠል ላይ ባለ ከሰል ላይ የተኛሁ ያህል ተሰማኝ፤ ሁለመናዬን የህመም አበላ ዋጠው፤ ሺ የማይታዩ መርፌዎች በሰውነቴ ላይ ተሰገሰጉብኝ፡፡ ቢሆንም ግን ለመጸለይ ሞከርኩ፡- ውድ እግዚአብሔር፣ ስለ እምነቴ መድከም ማረኝ… አምንሃለሁ… እንደምትምረንም አውቃለሁ፡፡ በዚህ ቤት ውስጥ ካለው ርኩስ መንፈስ ታይላለህ፡፡
ገዳዮቹ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ባየንበት ክፍል የቤት እቃዎቹን ያገላብጣሉ፤ የእኔንም ስም ደጋግመው ይጠራሉ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌን እንፈልጋታለን… ኢማኪዩሌን መግደያችን አሁን ነው፡፡››
ጆሮዎቼን በእጆቼ ይዤ ከገዳዮቹ ገጀራዎች አንዱ የኔ እንዲሆን፣ ጆሮዎቼንም ቆራርጬ መስማት እንዳቆም ተመኘሁ፡፡ ‹‹ወይ አምላኬ …›› ጮክ ብዬ መጸለይ ጀመርኩ፤ ምንም ቃላት ግን ማውጣት አልቻልኩም፡፡ ለመዋጥ ሞከርኩ፤ ጉሮሮዬ ግን ተዘጋ፡፡ ምንም ምራቅ አልነበረኝም፤ አፌም እንደኩበት ደርቋል፡፡ ዓይኖቼን ጨፈንኩ፡፡ ብጠፋም ተመኘሁ፤ ድምጹ ግን እየጨመረ መጣ፡፡ ምንም ዓይነት ምኅረት እንደማያደርጉልኝ አውቃለሁ፡፡ አእምሮዬም አንድ ሐሳብ ብቻ ያስተጋባ ጀመር - ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ መጽሐፍ ቅዱሴን በአፌ ያዝኩና በጥርሶቼ መካከል ጥብቅ አድርጌ ነከስኩት፡፡ የእግዚአብሔርን ቃላት ልውጣቸው ፈለግሁ፣ ወደ ነፍሴ ጥግ ጭልጥ አድርጌ ማስገባትንም ተመኘሁ፡፡ ጥንካሬውን በድጋሚ መፈለግ አሻኝ፣ ለረጅም ጊዜ ሲያስቸግረኝ የነበረው አሉታዊ ኃይል ግን በአእምሮዬ አስፈሪ ምስሎችን ያሳየኝ ይዟል፡፡ ገዳዮቹ ሲያገኙኝ ምን እንደሚያደርጉኝ ታየኝ - ግርፋቱን፣ ማሸማቀቁን ብሎም ግድያውን አየሁት….
ተው እግዚአብሔር፣ እባክህ! በጸጥታ ጮህኩ፡፡ በዚህ ውስጥ እንዳልፍ ምነው ፈለግህ? ለምን? ፍቅሬን ላንተ ለማሳየት ምን ላድርግ? አንተው እንደምታድነን ለማመን እፈልጋለሁ፡፡ ከዚህ የበለጠ እምነት እንዴት ሊኖረኝ ይችላል? በጣም
እየጸለይኩ ነው፣ እግዚአብሔር፣ በጣም… ግን በጣም ቀርበዋል፣ በቃ በጣም ደክሜያለሁ! እግዚአብሔር ሆይ… ደካክሜልሃለሁ፡፡
ራሴን የሳትኩ መሰለኝ - በቤቱ ዙሪያ የሚሰማው የገዳዮቹ ጆሮን እንደ መብረቅ የሚያደነቁር ድምጽ እስኪቀዛቀዝና በሩቅ የሚሰማ ሁካታ እስኪሆን ድረስ ራስን መግዛት የሚባል ነገር ከኔ ሸርተት አለ፡፡ ከዚያም ተኛሁ፤ የኢየሱስንም ጣፋጭ ሕልም አልም ገባሁ፡፡
ከሌሎቹ ሴቶች በላይም እንደ ላባ ተንሳፈፍኩ፡፡ ከበታቼ በወለሉም ላይ መጽሐፍ ቅዱሶቻቸውን በራሶቻቸው ላይ አድርገው እግዚአብሔርን ለምኅረት በመለማመን ሲንቀጠቀጡ አየኋቸው፡፡ ቀና ስል ኢየሱስን በወርቃማ ብርሃን ታጅቦ ከበላዬ ሲያንዣብብ አየሁት፤ እጆቹም ወደ እኔ ተዘርግተዋል፡፡ ፈገግ ስል ለሳምንታት ኩርምት ከማለቴ የተነሣ በሰውነቴ ላይ የነበሩት ቋሚ ሕመሞች ጠፉልኝ፡፡ ምንም ዓይነት ረሃብ፣ ጥምም ሆነ ፍርሃት የለ - በጣም ሰላም ተሰማኝ… ደስም አለኝ፡፡
ከዚያም ኢየሱስ ተናገረ፡ ‹‹ተራሮች በእምነት ይገፋሉ፣ ኢማኪዩሌ፣ እምነት ግን ቀላል ቢሆን ሁሉም ተራሮች ይሄዳሉ፡፡ በኔ ካመንሽብኝ መቼም ቢሆን እንደማልተውሽ እወቂ፡፡ በኔ እመኚ፣ ምንም ዓይነት ፍራቻም ዓይኑርሽ፡፡ በኔ እመኚ፤ አድንሽማለሁ፡፡ መስቀሌን በዚህ በር ላይ ስለማኖረው አይደርሱብሽም፡፡ እመኚብኝ፤ ትኖሪማለሽ፡፡››
ወደ ወለሉ በድንገት ተመልሼ ሌሎቹን ተቀላቀልኩ፡፡ ዓይኖቻቸውን አሁንም እንደጨፈኑ ነው፤ የኔ ዓይኖች ግን በመታጠቢያ ቤቱ በር ፊት ለፊት ከግንብ ግንብ በተንጣለለው አንጸባራቂ ነጭ የብርሃን መስቀል ላይ አፍጥጠው በሰፊው ተከፍተዋል፡፡ ሳየውም አንጸባራቂው ኃይል ፊቴን ነካው፤ እንደ ጸሐይ ሁሉ ቆዳዬንም አሞቀው፡፡ በደመ-ነፍስም ገዳዮቹን የሚመልስ አንዳች መለኮታዊ ኃይል ከመስቀሉ እየወጣ እንደሆነ አወቅሁ፡፡ እንደምንጠበቅና ደኅና እንደምንሆን ተገለጠልኝ፤ ስለሆነም የአንበሳ ጥንካሬ እንዳለኝ ሁሉ ተሰማኝ፤ ዘልዬም ቆምኩ፡፡ አምላኬን በፍቅሩ ድጋሚ ስለነካኝ አመሰገንኩት፤ ከዚያም ሌሎቹን ቁልቁል አየሁኋቸው፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ ቆይታዬ ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ አብረውኝ ባሉት ሰዎች ላይ ጮህኩባቸው፤ ‹‹ምንም አንሆንም! እመኑኝ… ሁሉም ነገር ጥሩ ይሆናል!›› የድምጼ ጉልህነት በፊታቸው ላይ እንደተሰነዘረ ጥፊ ሁሉ መታቸው፡፡ እንደ እብድ አይተውኝ ተንጠራርተው ወደ ወለሉ ሳቡኝ፡፡ ፈገግ አልኩ - ምንም እንኳን ከዚያ ወዲያ መስቀሉን በበሩ ላይ ማየት ባልችልም እዚያ እንዳለ ግን አውቃለሁ፡፡ ገዳዮቹ ከቤቱ ሄደዋል…. እየዘመሩ ሲሄዱም ሰምቻቸዋለሁ፡፡
ሌሊት ቄሱ ሊያዩን መጡ፡፡ ‹‹በቀጥታ የሄዱት ተንቀሳቃሽ ምስሉን ወዳሳየኋችሁ ስፍራ ነው›› ሲሉ አብራሩልን፡፡ ‹‹ክፍሉን ገነጣጠሉት፡፡ ምንም ማግኘት ሳይችሉ ሲቀሩ ሠራተኛዬን በድብደባ ሊቦጫጭቁት ምንም አልቀራቸው፡፡ ይቅርታ ጠይቀው ሄዱ፡፡ ቢሆንም ይህ ስፍራ ለእናንተ ደህንነት ከአሁን በኋላ ጥሩ አይደለም፡፡ ሠራተኛዬን አባርሬዋለሁ አሁን ተናዷል፤ ጥርጣሬም ገብቶታል፡፡ ከሌሎቹ ሠራተኞች ጋር ጓደኛ ስለሆነ ከአሁን በኋላ በእርግጠኝነት ሁሉም እያንዳንዷን እንቅስቃሴዬን ይከታተላሉ፡፡ ብቻ የፈረንሳይ ወታደሮች ወደ አካባቢያችን በቶሎ እንዲደርሱ ተስፋ እናድርግ
ቀጣዩን ሳምንት በሙሉ ተደናግጠን
፡
፡
#ምእራፍ_አስራ_አንድ
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#እምነቴን_ስጠብቅ
፡
፡
ገዳዮቹ ስሜን ሲጠሩ ሰምቻቸዋለሁ፡፡
የፍርሃት መአት በውስጤ ተሠራጨ፡፡ ዲያብሎስም ድጋሚ በጆሮዬ አንሾካሾከ - አሁን የት እንዳለሽ አውቀውታል… አሁን የት እንዳለሽ አውቀውታል… አእምሮዬ ወደ ድሮው ተመለሰና ራሴን ሳትኩ፡፡ ለምን ስሜን ተጣሩ - እዚህ እንዳለሁ እንዴት ሊያውቁ ቻሉ? ወደ መታጠቢያ ቤቱ እየመጡ ይሆን እንዴ?
አምላክን ለመጥራት ብሞክርም የምሰማው ብቸኛ ነገር ግን በቤቱ ከሚያስተጋቡት ከገዳዮቹ ክፉና አረመኔያዊ መዝሙሮች ጋር አእምሮዬን የተቆጣጠሩትን አሉታዊ ድምጾች ነው፡፡ ልብሶቼ በላብ ተጠምቀው እምነቴን ፍለጋ እፍጨረጨር ገባሁ፡፡
የመጡት በመቶዎች ሆነው ነው፡፡ ቄሱን የዛቻና የውንጀላ መዓት ያወርዱባቸዋል፡፡ ‹‹የት ነች?›› ሲሉ አንባረቁባቸው፡፡ ‹‹እዚህ እንዳለች እናውቃለን፡፡ ፈልጓት… ኢማኪዩሌን ፈልጓት፡፡››
ከግንቡ በስተጀርባ በቄሱ መኝታ ቤት ናቸው፡፡ ከግማሽ ጋት ያነሰ ውፍረት ያለው ጭቃና ዕንጨት ይለያየናል፡፡ እርምጃዎቻቸው ቤቱን አንቀጠቀጡት፣ ገጀራዎቻቸውና ጦሮቻቸውም ከግንቡ ጋር ሲጋጩ ይሰማኛል፡፡
በረብሻው መካከል አንድ የቤተሰቤ ወዳጅ የሆነን ሰው ድምፅ መለየት ቻልኩ፡፡ ‹‹399 በረሮዎችን ገድያለሁ›› በማለት ጉራውን ይነፋል፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ 400 ታደርግልኛለች፡፡ ይህም ቀላል የሚባል ቁጥር አይደለም፡፡››
በጥጋቷ እንደተሸሸግሁ ዲያብሎስ በጆሮዬ ይስቅብኛል፡፡ ስምሽን ያውቃሉ… እዚህ እንዳለሽ ያውቃሉ፡፡ አሁንስ አምላክሽ የት አለ?
ገዳዮቹ ቄሱን ተጫኗቸው፡- ‹‹ቱትሲዎቹ የት ናቸው? ካገኘናቸው ምን እንደምናደርጋቸው ታውቃለህ፡፡ የት አለች፤ ቄሱ፣ ኢማኪዩሌ የት ነች? መጨረሻ የታየችበት ስፍራ እዚህ ነው፡፡ የት ነው የደበቅሃት?››
መንፈሴ በፍርሃትና ጥርጣሬ ክንዶች ላይ ተመልሶ ወደቀ፡፡ እናም ገዳዮቹ መጀመሪያ በመጡበት ጊዜ ከፈራሁትም በላይ በጣም ፈራሁ፡፡ ድምጾቻቸው ሥጋዬን ሸነታተሩት፤ በመቀጣጠል ላይ ባለ ከሰል ላይ የተኛሁ ያህል ተሰማኝ፤ ሁለመናዬን የህመም አበላ ዋጠው፤ ሺ የማይታዩ መርፌዎች በሰውነቴ ላይ ተሰገሰጉብኝ፡፡ ቢሆንም ግን ለመጸለይ ሞከርኩ፡- ውድ እግዚአብሔር፣ ስለ እምነቴ መድከም ማረኝ… አምንሃለሁ… እንደምትምረንም አውቃለሁ፡፡ በዚህ ቤት ውስጥ ካለው ርኩስ መንፈስ ታይላለህ፡፡
ገዳዮቹ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ባየንበት ክፍል የቤት እቃዎቹን ያገላብጣሉ፤ የእኔንም ስም ደጋግመው ይጠራሉ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌን እንፈልጋታለን… ኢማኪዩሌን መግደያችን አሁን ነው፡፡››
ጆሮዎቼን በእጆቼ ይዤ ከገዳዮቹ ገጀራዎች አንዱ የኔ እንዲሆን፣ ጆሮዎቼንም ቆራርጬ መስማት እንዳቆም ተመኘሁ፡፡ ‹‹ወይ አምላኬ …›› ጮክ ብዬ መጸለይ ጀመርኩ፤ ምንም ቃላት ግን ማውጣት አልቻልኩም፡፡ ለመዋጥ ሞከርኩ፤ ጉሮሮዬ ግን ተዘጋ፡፡ ምንም ምራቅ አልነበረኝም፤ አፌም እንደኩበት ደርቋል፡፡ ዓይኖቼን ጨፈንኩ፡፡ ብጠፋም ተመኘሁ፤ ድምጹ ግን እየጨመረ መጣ፡፡ ምንም ዓይነት ምኅረት እንደማያደርጉልኝ አውቃለሁ፡፡ አእምሮዬም አንድ ሐሳብ ብቻ ያስተጋባ ጀመር - ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ ከያዙኝ ይገድሉኛል፡፡ መጽሐፍ ቅዱሴን በአፌ ያዝኩና በጥርሶቼ መካከል ጥብቅ አድርጌ ነከስኩት፡፡ የእግዚአብሔርን ቃላት ልውጣቸው ፈለግሁ፣ ወደ ነፍሴ ጥግ ጭልጥ አድርጌ ማስገባትንም ተመኘሁ፡፡ ጥንካሬውን በድጋሚ መፈለግ አሻኝ፣ ለረጅም ጊዜ ሲያስቸግረኝ የነበረው አሉታዊ ኃይል ግን በአእምሮዬ አስፈሪ ምስሎችን ያሳየኝ ይዟል፡፡ ገዳዮቹ ሲያገኙኝ ምን እንደሚያደርጉኝ ታየኝ - ግርፋቱን፣ ማሸማቀቁን ብሎም ግድያውን አየሁት….
ተው እግዚአብሔር፣ እባክህ! በጸጥታ ጮህኩ፡፡ በዚህ ውስጥ እንዳልፍ ምነው ፈለግህ? ለምን? ፍቅሬን ላንተ ለማሳየት ምን ላድርግ? አንተው እንደምታድነን ለማመን እፈልጋለሁ፡፡ ከዚህ የበለጠ እምነት እንዴት ሊኖረኝ ይችላል? በጣም
እየጸለይኩ ነው፣ እግዚአብሔር፣ በጣም… ግን በጣም ቀርበዋል፣ በቃ በጣም ደክሜያለሁ! እግዚአብሔር ሆይ… ደካክሜልሃለሁ፡፡
ራሴን የሳትኩ መሰለኝ - በቤቱ ዙሪያ የሚሰማው የገዳዮቹ ጆሮን እንደ መብረቅ የሚያደነቁር ድምጽ እስኪቀዛቀዝና በሩቅ የሚሰማ ሁካታ እስኪሆን ድረስ ራስን መግዛት የሚባል ነገር ከኔ ሸርተት አለ፡፡ ከዚያም ተኛሁ፤ የኢየሱስንም ጣፋጭ ሕልም አልም ገባሁ፡፡
ከሌሎቹ ሴቶች በላይም እንደ ላባ ተንሳፈፍኩ፡፡ ከበታቼ በወለሉም ላይ መጽሐፍ ቅዱሶቻቸውን በራሶቻቸው ላይ አድርገው እግዚአብሔርን ለምኅረት በመለማመን ሲንቀጠቀጡ አየኋቸው፡፡ ቀና ስል ኢየሱስን በወርቃማ ብርሃን ታጅቦ ከበላዬ ሲያንዣብብ አየሁት፤ እጆቹም ወደ እኔ ተዘርግተዋል፡፡ ፈገግ ስል ለሳምንታት ኩርምት ከማለቴ የተነሣ በሰውነቴ ላይ የነበሩት ቋሚ ሕመሞች ጠፉልኝ፡፡ ምንም ዓይነት ረሃብ፣ ጥምም ሆነ ፍርሃት የለ - በጣም ሰላም ተሰማኝ… ደስም አለኝ፡፡
ከዚያም ኢየሱስ ተናገረ፡ ‹‹ተራሮች በእምነት ይገፋሉ፣ ኢማኪዩሌ፣ እምነት ግን ቀላል ቢሆን ሁሉም ተራሮች ይሄዳሉ፡፡ በኔ ካመንሽብኝ መቼም ቢሆን እንደማልተውሽ እወቂ፡፡ በኔ እመኚ፣ ምንም ዓይነት ፍራቻም ዓይኑርሽ፡፡ በኔ እመኚ፤ አድንሽማለሁ፡፡ መስቀሌን በዚህ በር ላይ ስለማኖረው አይደርሱብሽም፡፡ እመኚብኝ፤ ትኖሪማለሽ፡፡››
ወደ ወለሉ በድንገት ተመልሼ ሌሎቹን ተቀላቀልኩ፡፡ ዓይኖቻቸውን አሁንም እንደጨፈኑ ነው፤ የኔ ዓይኖች ግን በመታጠቢያ ቤቱ በር ፊት ለፊት ከግንብ ግንብ በተንጣለለው አንጸባራቂ ነጭ የብርሃን መስቀል ላይ አፍጥጠው በሰፊው ተከፍተዋል፡፡ ሳየውም አንጸባራቂው ኃይል ፊቴን ነካው፤ እንደ ጸሐይ ሁሉ ቆዳዬንም አሞቀው፡፡ በደመ-ነፍስም ገዳዮቹን የሚመልስ አንዳች መለኮታዊ ኃይል ከመስቀሉ እየወጣ እንደሆነ አወቅሁ፡፡ እንደምንጠበቅና ደኅና እንደምንሆን ተገለጠልኝ፤ ስለሆነም የአንበሳ ጥንካሬ እንዳለኝ ሁሉ ተሰማኝ፤ ዘልዬም ቆምኩ፡፡ አምላኬን በፍቅሩ ድጋሚ ስለነካኝ አመሰገንኩት፤ ከዚያም ሌሎቹን ቁልቁል አየሁኋቸው፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ ቆይታዬ ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ አብረውኝ ባሉት ሰዎች ላይ ጮህኩባቸው፤ ‹‹ምንም አንሆንም! እመኑኝ… ሁሉም ነገር ጥሩ ይሆናል!›› የድምጼ ጉልህነት በፊታቸው ላይ እንደተሰነዘረ ጥፊ ሁሉ መታቸው፡፡ እንደ እብድ አይተውኝ ተንጠራርተው ወደ ወለሉ ሳቡኝ፡፡ ፈገግ አልኩ - ምንም እንኳን ከዚያ ወዲያ መስቀሉን በበሩ ላይ ማየት ባልችልም እዚያ እንዳለ ግን አውቃለሁ፡፡ ገዳዮቹ ከቤቱ ሄደዋል…. እየዘመሩ ሲሄዱም ሰምቻቸዋለሁ፡፡
ሌሊት ቄሱ ሊያዩን መጡ፡፡ ‹‹በቀጥታ የሄዱት ተንቀሳቃሽ ምስሉን ወዳሳየኋችሁ ስፍራ ነው›› ሲሉ አብራሩልን፡፡ ‹‹ክፍሉን ገነጣጠሉት፡፡ ምንም ማግኘት ሳይችሉ ሲቀሩ ሠራተኛዬን በድብደባ ሊቦጫጭቁት ምንም አልቀራቸው፡፡ ይቅርታ ጠይቀው ሄዱ፡፡ ቢሆንም ይህ ስፍራ ለእናንተ ደህንነት ከአሁን በኋላ ጥሩ አይደለም፡፡ ሠራተኛዬን አባርሬዋለሁ አሁን ተናዷል፤ ጥርጣሬም ገብቶታል፡፡ ከሌሎቹ ሠራተኞች ጋር ጓደኛ ስለሆነ ከአሁን በኋላ በእርግጠኝነት ሁሉም እያንዳንዷን እንቅስቃሴዬን ይከታተላሉ፡፡ ብቻ የፈረንሳይ ወታደሮች ወደ አካባቢያችን በቶሎ እንዲደርሱ ተስፋ እናድርግ
ቀጣዩን ሳምንት በሙሉ ተደናግጠን
👍2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሁለት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#አዲስ_መንገድ
፡
፡
#የነጻነት_ሕመም
፡
የምሽቱ ድባብ የማልቆጣጠረው ስሜት አሳደረብኝ፡፡ የአየሩ ቅዝቃዜ ቆዳዬን ሲነካው፣ ለሳንባዎቼ አየሩ ሲቀላቸው፣ በዓይኔ ላይ የሚጨፍሩት እልፍ አዕላፍ ክዋክብት በውበታቸው ሲያፈዙኝ ነፍሴን ‹‹ተመስገን አምላኬ!›› ብላ እንድትዘምር አደረጓት፡፡
‹‹ምን ላይ ነው ያፈጠጥሺው? እንሂድ እንጂ - በአስቸኳይ መሄድ
አለብን!›› ሲሉ የመጀመሪያዋን የነጻነት መጠጥ እንደተጎነጨሁ ቄስ ሙሪንዚ ትዕግሥት አጥተው ሾር ብዬ እንድሄድ ተናገሩ፡፡ ቄሱ ከሌሎቹ ሴቶችና ወደ ፈረንሳዮች ምሽግ አብሮን ሊሄድ ከተነሣው ከዮሃንስ ጋር በሩ ጋ ይጠብቁናል፡፡ ዮሃንስ በጣም አረፈደ እንጂ መባነኑና እፊት እፊት ማለቱ ባልከፋ፡፡ በዚህ ጊዜ ከዘር ጭፍጨፋው መትረፌንም ሆነ ንጋትን እንደገና ለማየት መቻሌን አላወቅሁም - የግንኙነታችንም መሞት አልታወቀኝ፡፡ ቄሱ በራቸውን ሲከፍቱት ከቤት ወንድ ልጆቻቸው (ከሴምቤባ በስተቀር) ጦሮች፣ ቢላዎችና ቀስቶች ይዘው ወጡ፡፡ ዙሪያችንን በሚገባ ከበው በሩን አስወጡን፡፡ ከጠርጣራ ወንድ የቤት ሠራተኞቻቸውና ክፉ ጎረቤቶቻቸው አደገኛ ዓይኖች ከለሉን፡፡ ከዚያም ወደ ውጪ ወጣንና ወደ መታጠቢያ ቤቱ ከሦስት ወራት በፊት ባመጣኝ በአቧራማው የእግር መንገድ በፍጥነት ተራመድን፡፡ ዓይኖቼ ጨለማውን እየተላመዱት ሲሄዱም ቄስ ሙሪንዚም ሆኑ ዮሃንስ እንደታጠቁ አየሁ፤ ዮሃንስ ረጅም ጦር የያዘ ሲሆን ቄሱ በበኩላቸው ጠመንጃቸውን በትከሻቸው አንግተዋል፡፡ የገዳዮች ቡድን መንገዳችን ላይ ቢያጋጥመን ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ አሰብኩ፡፡ ሰዎች በመንገዱ ሌላኛው አቅጣጫ ከጨለማው ውስጥ ብቅ ሲሉ በድንገት አየናቸው፡፡ ምን አልባትም 60 የሚሆኑ ኢንተርሃምዌዎች በሁለት መስመሮች በሰልፍ ይመጣሉ፡፡ አስፈሪ የደንብ ልብሶቻቸውን ያልለበሱ ቢሆንም ቅሉ ትዕይንቱ ያስበረግጋል፡- እስካፍንጫቸው ታጥቀው በፍጥነት ይጓዛሉ፤ ገጀራዎችን፣ ጠመንጃዎችን፣ ቦንቦችን፣ ጦሮችንና ረጃጅም ማረጃ ቢላዎቻቸውን ይዘው ወደ እኛ በመጠጋት ላይ ናቸው - አንደኛው እንዲያውም ቀስት ይዟል፡፡በአጠገባቸው በጣም ተጠግተን ስለሄድን እንዲያውም የሰውነታቸውን ጠረንና ከትንፋሻቸው የሚመጣውን የሚተናፈግ አልኮል ሳይቀር ማሽተት ችያለሁ፡፡ በሚገርም ሁኔታ በመታጠቢያ ቤቱ ከእነርሱ ተደብቄ ከነበርኩበት ጊዜ ይልቅ በአጠገባቸው ሳልፍ በአንጻራዊነት ፍርሃቴ ቀንሷል፡፡ በዚህም ጊዜ እግዚአብሔርን በደኅና እንዲያቆየንና ፍራቻዬን እንዲያረግብልኝ ለመንኩት፡፡
ሌሎቹ ሴቶችና እኔ ኢንተርሃምዌዎቹ ሴቶች መሆናችንን እንዳይለዩ በማለት በቡድን አጀባችን መካከል ራሳችንን ዝቅ አደረግን፡፡ ያለ ምንም ችግርም አለፍን፡፡ እንዲያውም የተወሰኑት ገዳዮች ሰላምታ አቀረቡልን፤ ሲያልፉም ለዮሃንስና ለቄሱ መልካም ዕድል ተመኙላቸው፡፡ አንድም እኛን ሌሊት ድረስ ቆይተን እያደንን ያለን ገዳዮች አድርገው አስበውናል አለያም አምላክ ዓይናቸውን አሳውሯቸዋል … ሁለቱም ምክንያት እንደሆነ አሰብኩ፡፡ በተጨማሪም አሁን ባለው የዘር ፍጅቱ ደረጃ ይህን ያህል ቁጥር ያላቸው ቱትሲዎች በአንድ ቦታ በሕይወት ይኖራሉ ብለው አልጠበቁም፤ ወይንም አላመኑም፡፡ በየመንገዱ አስከሬኖች ስለወደቁ እንደዚያ ብለው ለማመን ጥሩ ምክንያት ነበራቸው፡፡
አምላክ ለጸሎቴ ምላሽ ሰጠኝ፡፡ ለገዳዮቹ ያለኝንም ፍራቻ አሽቀንጥሮ ጣለልኝ፡፡ ግን ከሁኔታው ሳየው ጌታ ለቄስ ሙሪንዚና ለዮሃንስ ተመሳሳይ በረከት ያጋራቸው አይመስልም፡፡ ኢንተርሃምዌዎችን በማግኘታችን ሁለቱም ተደናግጠዋል፡፡ ዮሃንስና ቄስ ሙሪንዚ ገዳዮቹ ከእይታችን እንደተሰወሩ የገቡበትን ጣጣ እንደገና አጤኑት፡፡ ቄሱ ‹‹እናንተ ሴቶች ከዚህ በኋላ ብቻችሁን ሂዱ›› አሉን፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ከዚህ ቅርብ ናቸው… ሂዱ ቀጥሉ፤ ከእይታችን እስክትሰወሩ እናያችኋለን፡፡›› ቄሱና እኔ በፍጥነት ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ እርሳቸው፣ ወንዶች ልጆቻቸውና ዮሃንስ ከመንገዱ ወደ ጥሻ ውስጥ ለመደበቅ በችኮላ ሄዱ፡፡ ያኔ ሌሎቹ ሴቶችና እኔ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ቦታ ላይ ስለሆንን የምናባክነው ምንም ዓይነት ጊዜ አልነበረንም፡፡ የፈረንሳውያኑ ምሽግ 500 እርምጃዎች ገደማ ይርቃል፤ ስለሆነም እግሮቻችን በቻሉት መጠን በፍጥነት ተጓዝን፡፡
የተተወ የወንጌላውያን ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በተቋቋመው ምሽግ ጋ ስንደርስ ልቤ ድው ድው ይል ጀመር፡፡ የተቀረው ቡድን ከዋናው በር ፊት ለፊት በጣም ፈርቶ ተመስጎ ሳለ እኔ በቻልኩት መጠን በሩን እደበድብና በጣም ጮኬ
‹‹እባካችሁ እርዱን! እባካችሁ እገዛችሁን እንፈልጋለን!›› እል ጀመር፡፡ ከሹክሹክታ በላይ ከተናገርኩ በጣም ረጅም ጊዜ ስለሆነኝ ለመጮህ ካደረግሁት ጥረት የተነሣ ጉሮሮዬን አመመኝ፡፡ ድምጼ የታፈነና በጣም ዝግ ያለ ስለሆነ አይሰማም ለማለት ይቻላል፡፡ ሊያድነን የሚጠብቀን ማንም ሰው ሳናገኝ ስንቀር ሴቶቹ በፍርሃት ራዱ፤ ለቅሶና እዬዬም ጀመሩ፡፡ ከአፍታ በኋላ ስድስት ወይም ሰባት ወታደሮች መትረየሶቻቸውን ወደ እኛ ደግነው በአጥሩ በአንደኛው አቅጣጫ ብቅ አሉ፡፡ ፈረንሳይኛ የምናገረው እኔ ብቻ ስለሆንኩ ባልንጀሮቼን ዝም አስባልኩና ለወታደሮቹ ስለማንነታችንና ስለአመጣጣችን ነገርኳቸው፡፡
ወታደሮቹም በጥርጣሬ ተመለከቱን፣ ጠመንጃዎቻቸውንም እንዳቀባበሉ ናቸው፡፡ ‹‹እውነት ነው! የነገርኳችሁ ሁሉ እውነት ነው… ታድኑን ዘንድ እናንተን ስንጠብቅ ቆይተናል›› አልኳቸው በተስፋ መቁረጥ፡፡
በቡድኑ ውስጥ ካሉት ወታደሮች ትንሹ፣ ኮስታራው፣ መልኩ ፈገግ ያለውና ጸጉሩን የተላጨው ሰውዬ ወደ ዋናው በር መጥቶ በፊታችን ላይ ባትሪ አበራብን፡፡ የአፍንጮቻችንን ቅርጽ እየተመለከተ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ነባሩ አስተሳሰብ ሁቱዎች ደፍጣጣ ቱትሲዎች ደግሞ ሰልካካ አፍንጫ አላቸው የሚል ነው፡፡ ስለሆነም ፈተናውን አልፈን ሳይሆን አይቀርም በሩን ከፍቶ አስገባን፡፡ ይሁን እንጂ መታወቂያ ደብተሮቻችንን ለማየት ሲጠይቀንም መሣሪያውን እንደደገነ ነው፡፡ሴቶቹ በኃይል ሲተነፍሱ ይሰማኛል - ማናቸውም ቢሆኑ መታወቂያዎቻቸውን አልያዙም፡፡ በዚህም ምክንያት ፈረንሳውያኑ እዚያው የሚረሽኗቸው መስሏቸዋል፡፡ ደግነቱ በኔ በኩል መታወቂያዬን ከሦስት ወር በፊት ቤቴን ለቅቄ ስወጣ በኋላ ኪሴ ይዤዋለሁ፡፡ ወታደሩ ቱትሲ የሚል ቃል ከዳር እስከዳር የታተመበትን የኔን መታወቂያ አይቶ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ፡፡ ወዲያውኑ ለሌሎቹ ሴቶች በእርግጠኝነት
‹‹ምንም የምንሆን አይመስለኝም›› ስል አረጋገጥኩላቸው፡፡
ለወራት የታመቀ ፍራቻ፣ ብስጭትና ሥጋት ከነፍሳችን ወንዝ ፈሰሰ፤ በውስጣችን ያለው የስሜት ግድብ ፈረሰ፤ የተወሰኑት ሴቶች ሊቆጣጠሩት በማይችሉት መልኩ አለቀሱ፡፡ የወታደሮቹም አቀራረብ ከዚያ በኋላ ተቀየረ - ድምጻቸው በደግነትና በያገባኛል ስሜት ተሞልቶ ጠመንጃዎቻቸውን ዝቅ አድርገው በሐዘኔታ ያነጋገሩን ጀመር፡፡ በወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየነው የታሸገ ውሃና አይብ ተሰጠን፡፡ ቄሱ እንደገመቱት ፈረንሳውያኑ እንደማይገድሉን አውቀን በጣም ሰፍ ብለን መጉረስ ጀመርን፡፡
‹‹አይዟችሁ ምንም ችግር የለም›› አለ ትንሹ ወታደር፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ ቅንጣት ታክል ልትጨነቁ አይገባችሁም … ቅዠታችሁ አክትሟል፡፡ ማንም ሰው እንዲጎዳችሁ አንፈቅድም፡፡ ገባችሁ? ምንም ሥጋት አይግባችሁ፤
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሁለት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#አዲስ_መንገድ
፡
፡
#የነጻነት_ሕመም
፡
የምሽቱ ድባብ የማልቆጣጠረው ስሜት አሳደረብኝ፡፡ የአየሩ ቅዝቃዜ ቆዳዬን ሲነካው፣ ለሳንባዎቼ አየሩ ሲቀላቸው፣ በዓይኔ ላይ የሚጨፍሩት እልፍ አዕላፍ ክዋክብት በውበታቸው ሲያፈዙኝ ነፍሴን ‹‹ተመስገን አምላኬ!›› ብላ እንድትዘምር አደረጓት፡፡
‹‹ምን ላይ ነው ያፈጠጥሺው? እንሂድ እንጂ - በአስቸኳይ መሄድ
አለብን!›› ሲሉ የመጀመሪያዋን የነጻነት መጠጥ እንደተጎነጨሁ ቄስ ሙሪንዚ ትዕግሥት አጥተው ሾር ብዬ እንድሄድ ተናገሩ፡፡ ቄሱ ከሌሎቹ ሴቶችና ወደ ፈረንሳዮች ምሽግ አብሮን ሊሄድ ከተነሣው ከዮሃንስ ጋር በሩ ጋ ይጠብቁናል፡፡ ዮሃንስ በጣም አረፈደ እንጂ መባነኑና እፊት እፊት ማለቱ ባልከፋ፡፡ በዚህ ጊዜ ከዘር ጭፍጨፋው መትረፌንም ሆነ ንጋትን እንደገና ለማየት መቻሌን አላወቅሁም - የግንኙነታችንም መሞት አልታወቀኝ፡፡ ቄሱ በራቸውን ሲከፍቱት ከቤት ወንድ ልጆቻቸው (ከሴምቤባ በስተቀር) ጦሮች፣ ቢላዎችና ቀስቶች ይዘው ወጡ፡፡ ዙሪያችንን በሚገባ ከበው በሩን አስወጡን፡፡ ከጠርጣራ ወንድ የቤት ሠራተኞቻቸውና ክፉ ጎረቤቶቻቸው አደገኛ ዓይኖች ከለሉን፡፡ ከዚያም ወደ ውጪ ወጣንና ወደ መታጠቢያ ቤቱ ከሦስት ወራት በፊት ባመጣኝ በአቧራማው የእግር መንገድ በፍጥነት ተራመድን፡፡ ዓይኖቼ ጨለማውን እየተላመዱት ሲሄዱም ቄስ ሙሪንዚም ሆኑ ዮሃንስ እንደታጠቁ አየሁ፤ ዮሃንስ ረጅም ጦር የያዘ ሲሆን ቄሱ በበኩላቸው ጠመንጃቸውን በትከሻቸው አንግተዋል፡፡ የገዳዮች ቡድን መንገዳችን ላይ ቢያጋጥመን ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ አሰብኩ፡፡ ሰዎች በመንገዱ ሌላኛው አቅጣጫ ከጨለማው ውስጥ ብቅ ሲሉ በድንገት አየናቸው፡፡ ምን አልባትም 60 የሚሆኑ ኢንተርሃምዌዎች በሁለት መስመሮች በሰልፍ ይመጣሉ፡፡ አስፈሪ የደንብ ልብሶቻቸውን ያልለበሱ ቢሆንም ቅሉ ትዕይንቱ ያስበረግጋል፡- እስካፍንጫቸው ታጥቀው በፍጥነት ይጓዛሉ፤ ገጀራዎችን፣ ጠመንጃዎችን፣ ቦንቦችን፣ ጦሮችንና ረጃጅም ማረጃ ቢላዎቻቸውን ይዘው ወደ እኛ በመጠጋት ላይ ናቸው - አንደኛው እንዲያውም ቀስት ይዟል፡፡በአጠገባቸው በጣም ተጠግተን ስለሄድን እንዲያውም የሰውነታቸውን ጠረንና ከትንፋሻቸው የሚመጣውን የሚተናፈግ አልኮል ሳይቀር ማሽተት ችያለሁ፡፡ በሚገርም ሁኔታ በመታጠቢያ ቤቱ ከእነርሱ ተደብቄ ከነበርኩበት ጊዜ ይልቅ በአጠገባቸው ሳልፍ በአንጻራዊነት ፍርሃቴ ቀንሷል፡፡ በዚህም ጊዜ እግዚአብሔርን በደኅና እንዲያቆየንና ፍራቻዬን እንዲያረግብልኝ ለመንኩት፡፡
ሌሎቹ ሴቶችና እኔ ኢንተርሃምዌዎቹ ሴቶች መሆናችንን እንዳይለዩ በማለት በቡድን አጀባችን መካከል ራሳችንን ዝቅ አደረግን፡፡ ያለ ምንም ችግርም አለፍን፡፡ እንዲያውም የተወሰኑት ገዳዮች ሰላምታ አቀረቡልን፤ ሲያልፉም ለዮሃንስና ለቄሱ መልካም ዕድል ተመኙላቸው፡፡ አንድም እኛን ሌሊት ድረስ ቆይተን እያደንን ያለን ገዳዮች አድርገው አስበውናል አለያም አምላክ ዓይናቸውን አሳውሯቸዋል … ሁለቱም ምክንያት እንደሆነ አሰብኩ፡፡ በተጨማሪም አሁን ባለው የዘር ፍጅቱ ደረጃ ይህን ያህል ቁጥር ያላቸው ቱትሲዎች በአንድ ቦታ በሕይወት ይኖራሉ ብለው አልጠበቁም፤ ወይንም አላመኑም፡፡ በየመንገዱ አስከሬኖች ስለወደቁ እንደዚያ ብለው ለማመን ጥሩ ምክንያት ነበራቸው፡፡
አምላክ ለጸሎቴ ምላሽ ሰጠኝ፡፡ ለገዳዮቹ ያለኝንም ፍራቻ አሽቀንጥሮ ጣለልኝ፡፡ ግን ከሁኔታው ሳየው ጌታ ለቄስ ሙሪንዚና ለዮሃንስ ተመሳሳይ በረከት ያጋራቸው አይመስልም፡፡ ኢንተርሃምዌዎችን በማግኘታችን ሁለቱም ተደናግጠዋል፡፡ ዮሃንስና ቄስ ሙሪንዚ ገዳዮቹ ከእይታችን እንደተሰወሩ የገቡበትን ጣጣ እንደገና አጤኑት፡፡ ቄሱ ‹‹እናንተ ሴቶች ከዚህ በኋላ ብቻችሁን ሂዱ›› አሉን፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ከዚህ ቅርብ ናቸው… ሂዱ ቀጥሉ፤ ከእይታችን እስክትሰወሩ እናያችኋለን፡፡›› ቄሱና እኔ በፍጥነት ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ እርሳቸው፣ ወንዶች ልጆቻቸውና ዮሃንስ ከመንገዱ ወደ ጥሻ ውስጥ ለመደበቅ በችኮላ ሄዱ፡፡ ያኔ ሌሎቹ ሴቶችና እኔ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ቦታ ላይ ስለሆንን የምናባክነው ምንም ዓይነት ጊዜ አልነበረንም፡፡ የፈረንሳውያኑ ምሽግ 500 እርምጃዎች ገደማ ይርቃል፤ ስለሆነም እግሮቻችን በቻሉት መጠን በፍጥነት ተጓዝን፡፡
የተተወ የወንጌላውያን ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በተቋቋመው ምሽግ ጋ ስንደርስ ልቤ ድው ድው ይል ጀመር፡፡ የተቀረው ቡድን ከዋናው በር ፊት ለፊት በጣም ፈርቶ ተመስጎ ሳለ እኔ በቻልኩት መጠን በሩን እደበድብና በጣም ጮኬ
‹‹እባካችሁ እርዱን! እባካችሁ እገዛችሁን እንፈልጋለን!›› እል ጀመር፡፡ ከሹክሹክታ በላይ ከተናገርኩ በጣም ረጅም ጊዜ ስለሆነኝ ለመጮህ ካደረግሁት ጥረት የተነሣ ጉሮሮዬን አመመኝ፡፡ ድምጼ የታፈነና በጣም ዝግ ያለ ስለሆነ አይሰማም ለማለት ይቻላል፡፡ ሊያድነን የሚጠብቀን ማንም ሰው ሳናገኝ ስንቀር ሴቶቹ በፍርሃት ራዱ፤ ለቅሶና እዬዬም ጀመሩ፡፡ ከአፍታ በኋላ ስድስት ወይም ሰባት ወታደሮች መትረየሶቻቸውን ወደ እኛ ደግነው በአጥሩ በአንደኛው አቅጣጫ ብቅ አሉ፡፡ ፈረንሳይኛ የምናገረው እኔ ብቻ ስለሆንኩ ባልንጀሮቼን ዝም አስባልኩና ለወታደሮቹ ስለማንነታችንና ስለአመጣጣችን ነገርኳቸው፡፡
ወታደሮቹም በጥርጣሬ ተመለከቱን፣ ጠመንጃዎቻቸውንም እንዳቀባበሉ ናቸው፡፡ ‹‹እውነት ነው! የነገርኳችሁ ሁሉ እውነት ነው… ታድኑን ዘንድ እናንተን ስንጠብቅ ቆይተናል›› አልኳቸው በተስፋ መቁረጥ፡፡
በቡድኑ ውስጥ ካሉት ወታደሮች ትንሹ፣ ኮስታራው፣ መልኩ ፈገግ ያለውና ጸጉሩን የተላጨው ሰውዬ ወደ ዋናው በር መጥቶ በፊታችን ላይ ባትሪ አበራብን፡፡ የአፍንጮቻችንን ቅርጽ እየተመለከተ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ነባሩ አስተሳሰብ ሁቱዎች ደፍጣጣ ቱትሲዎች ደግሞ ሰልካካ አፍንጫ አላቸው የሚል ነው፡፡ ስለሆነም ፈተናውን አልፈን ሳይሆን አይቀርም በሩን ከፍቶ አስገባን፡፡ ይሁን እንጂ መታወቂያ ደብተሮቻችንን ለማየት ሲጠይቀንም መሣሪያውን እንደደገነ ነው፡፡ሴቶቹ በኃይል ሲተነፍሱ ይሰማኛል - ማናቸውም ቢሆኑ መታወቂያዎቻቸውን አልያዙም፡፡ በዚህም ምክንያት ፈረንሳውያኑ እዚያው የሚረሽኗቸው መስሏቸዋል፡፡ ደግነቱ በኔ በኩል መታወቂያዬን ከሦስት ወር በፊት ቤቴን ለቅቄ ስወጣ በኋላ ኪሴ ይዤዋለሁ፡፡ ወታደሩ ቱትሲ የሚል ቃል ከዳር እስከዳር የታተመበትን የኔን መታወቂያ አይቶ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ፡፡ ወዲያውኑ ለሌሎቹ ሴቶች በእርግጠኝነት
‹‹ምንም የምንሆን አይመስለኝም›› ስል አረጋገጥኩላቸው፡፡
ለወራት የታመቀ ፍራቻ፣ ብስጭትና ሥጋት ከነፍሳችን ወንዝ ፈሰሰ፤ በውስጣችን ያለው የስሜት ግድብ ፈረሰ፤ የተወሰኑት ሴቶች ሊቆጣጠሩት በማይችሉት መልኩ አለቀሱ፡፡ የወታደሮቹም አቀራረብ ከዚያ በኋላ ተቀየረ - ድምጻቸው በደግነትና በያገባኛል ስሜት ተሞልቶ ጠመንጃዎቻቸውን ዝቅ አድርገው በሐዘኔታ ያነጋገሩን ጀመር፡፡ በወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየነው የታሸገ ውሃና አይብ ተሰጠን፡፡ ቄሱ እንደገመቱት ፈረንሳውያኑ እንደማይገድሉን አውቀን በጣም ሰፍ ብለን መጉረስ ጀመርን፡፡
‹‹አይዟችሁ ምንም ችግር የለም›› አለ ትንሹ ወታደር፡፡ ‹‹ከዚህ በኋላ ቅንጣት ታክል ልትጨነቁ አይገባችሁም … ቅዠታችሁ አክትሟል፡፡ ማንም ሰው እንዲጎዳችሁ አንፈቅድም፡፡ ገባችሁ? ምንም ሥጋት አይግባችሁ፤
👍2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሦስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ከዳማሲን_የተላከ_ደብዳቤ
፡
፡
ከትምህርት ቤቱ በስተጀርባ ብቻዬን ሆኜ የዳማሲንን ደብዳቤ ከፈትኩት፡፡ ለማንበብ የሚያስቸግረውን የእጅ ጽሑፉን እንዳየሁ በትምህርት ቤት እንዳለን የጻፈልኝን ደብዳ ቤዎች ሁሉ አስታውሼ ልቤ ታመመ፡፡ ፈጽሞ ግልጽ ስሜት የማይንጸባረቅባቸው፣ ግን ሁሌ በፍቅርና በደግነት፣ በማበረታቻና አድናቆት፣ በግሩም ምክርና ረጋ ያለ ተግሳጽ፣ ስለ ወዳጆቻችን በሚያወሱ ወሬዎችና በብዙ ቀልዶች የተሞሉ ደብዳቤዎቹ ትውስ አሉኝ፡፡ ጀርባዬን በትምህርት ቤቱ ክፍል ግድግዳ ላይ አስደግፌ ተቀምጬ አነብ ጀመር፡፡
ግንቦት 6፣ 1994
ውድ (አባባ፣ እማማ፣ ቪያኒ እና) ኢማኪዩሌ ሁላችንም ከተለያየን አንድ ወር ገደማ ሆነን፡፡ ይሄው የቅዠት ኑሮ እየኖርን ነው፡፡ ሁናቴዎች ከሚያሳዩት ነገር ባሻገር አንድ ዘውግ ሌላውን ፈጽሞ የሚያጠፋው የእግዚአብሔር ፍቃድ ሲሆን ብቻ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምናልባት የእኛ ሕይወት ለሩዋንዳ ድኅነት እንዲከፈል ግድ ብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለ አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ - እንደገና እንደምንገናኝ በአእምሮዬ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለም፡፡
ከሀገሪቱ ለመውጣት ልሞክር ነው፣ ግን ይሳካልኝ አይሳካልኝ አላውቅም፡፡ በመንገድ ላይ ከገደሉኝ ስለ እኔ አትጨነቁ፤ በሚገባ ጸልያለሁ . . . ለሞትም ተዘጋጅቻለሁ፡፡ ከሩዋንዳ መውጣት ከቻልኩ ሰላም እንደተመለሰ ወዲያውኑ ሁላችሁንም አገኛችኋለሁ፡፡ የደረሰብኝን ሁሉ ቦን
ይነግራችኋል፡፡
የዳማሲን ጓደኛ ቦን በሌላ ጊዜ እንደነገረኝ ወንድሜ ደብዳቤውን እየጻፈ ሳለ እዚህ ሐሳብ ላይ ሲደርስ ዳማሲን ብዕሩን ቁጭ አድርጎ ቀና ብሎ እያየው ‹‹ቦን፣ ወዳጄ እንደሆንክ አውቃለሁ፤ ስሜቴም ሳይጎዳ እንዲቆይ ሞክረሃል፣ አሁን ልትነግረኝ የሚገባህ ሰዓት ላይ ነን - ከቤተሰቤ አባላት የተገደለ አለ እንዴ?›› ቦን ሁቱ ስለሆነ በዘር ጭፍጨፋው ወቅት በነጻነት ይጓጓዝና በአካባቢው ከቱትሲዎች ማንኛቸው እንደተገደሉ ያውቃል፡፡ የወላጆቼንና የቪያኒን ሞት ለራሱ በምስጢር የያዘው ለወንድሜ በጣም ስለሚጠነቀቅለትና ስሜቱን ሳይጎዳ ለመጠበቅ ስለፈለገ ነው፡፡
ዳማሲን በቀጥታ ሲጠይቀው ጊዜ ቦን ከባዱን መርዶ አረዳው፡፡ ጓደኛው የሚወዳቸው የቤተሰቡ አባላት ገና በሕይወት ያሉ እየመሰለው ደብዳቤውን መጻፉን እስኪጨርስ መጠበቅን አልፈለገም፡፡ ስለዚህ ቦን ለዳማሲን አባታችን፣ እናታችንና ታናሽ ወንድማችን እንደተገደሉና እኔ ምናልባት በሕይወት ተርፌ ሊሆን እንደሚችል ይነግረዋል፡፡ ዳማሲን ቀኑን ሙሉ ማለት ይቻላል አልቅሶ እንደነበር የደብዳቤው ቋሚ ምልክት የሆኑት የእንባ ጠብታዎች ይህንን ይመሰክራሉ፡፡
ዳማሲን ኪቩ ሐይቅን ለማቋረጥ ጀልባ ፍለጋ ከመሄዱ በፊት ደብዳቤውን እንደገና አውጥቶ አባባ፣ እማማና ቪያኒ በሚሉት ቃላት ግራና ቀኝ ቅንፎችን አስቀምጦ የሚከተሉትን አረፍተ ነገሮች አከለ፡፡ ኢማኪዩሌ እንድትጠነክሪ እለምንሻለሁ፡፡ እማማ፣ አባባና ቪያኒ መገደላቸውን አሁን ሰማሁ፡፡ በተቻለኝ ፍጥነት ላገኝሽ እሞክራለሁ፡፡ ራስሽን ሳሚልኝ፤ እቀፊልኝም! በጣም የሚወድሽ ወንድምሽ!
ይህ ካነበብኳቸው ነገሮች ሁሉ የሚሠቀጥጠው ነው፡፡ እንባ ባረጠባቸው ቃላት ላይ የጣቶቼን ጫፎች አላወስኳቸውና ይህንን ደብዳቤ ሳላለቅስ ማንበብ እንደማልችል ተረዳሁ፡፡
በኋላ ላይ እንደደረስኩበት ለዘላለም የኔ ጀግና ሆኖ የሚኖረው ቦን ወንድሜን በቤቱ ከቤተሰቡ ፍላጎት በተጻራሪ ሊሸሽገው ሞክሯል፡፡ በዘር ፍጅቱ የመጀመሪያ ቀናት ዳማሲንን በምስጢር ከአልጋው ስር በደኅና በመደበቅ ሊያቆየው ችሎ ነበር፡፡ የቦን ቤተሰብ ግን ያደረገውን ነገር ሲደርስበት ዳማሲንን ለገዳዮቹ እንዲሰጥ ግፊት ያሳድርበታል፡፡
ይባስ ብሎ ቱትሲ ልጆችን በዘውግ ስም ጥሪ ወቅት ማሸማቀቅ የሚወደው ቡሆሮ ከቦን አጎቶች አንዱ ነው፡፡ ቡሆሮ በሀገሪቱ ወስጥ ካሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ውስጥ አንዱ፣ መጥፎና አደገኛ ገዳይ ሆኖ ነበርና ሲጠራጠርበት ጊዜ ቦን ዳማሲንን በጭራሽ ቤት ውስጥ ማቆየት እንደሌለበት ይረዳል፡፡ አንድ ሌሊትም በጣም አምሽቶ በቤተሰቡ መሬት ራቅ ያለ ጥግ ላይ ጉድጓድ ቆፍሮ በዕንጨትና ቅጠላቅጠል ይሸፍነዋል፡፡ ገዳዮቹ በቡሆሮ ተጠቁመው ከመምጣታቸው በፊት ዳማሲንንም በጥንቃቄ ከመኝታ ክፍሉ ያስወጣና በጉድጓዱ ውስጥ ይደብቀዋል ፡፡
ዳማሲን በጉድጓድ ውስጥ ከሦስት ሳምንታት ለበለጠ ጊዜ ያህል ተደብቆ ሳለ ገዳዮቹ በቡሆሮ ውትወታ በተደጋጋሚ የቦንን ቤት አሠሡ፡፡ እነዚህ አራጆች ግን የማይሰለቹ በመሆናቸው የቦንን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ተከታትለው መጨረሻ ላይ ምግብ ወደ ውጪ ይዞ ሲሄድ ያዩታል፡፡ ሸሻጊው ጓደኛውና ተሸሻጊው ዳማሲን ገዳዮቹ ግቢውን ሊያስሱብን ይችላሉ ብለው ሠግተው ዳማሲን የኪቩ ሐይቅን ተሻግሮ ወደ ዛየር እንዲያቀና ይወስናሉ፡፡ (ቦን የቱትሲዎችን ሕይወት ለማትረፍ ሐይቁን የሚያሻግራቸውን አንድ ደግ ሳምራዊ ዐሳ አጥማጅ ሁቱ ያውቃል፡፡) ዳማሲንን ከጉድጓዱ አውጥቶ በየጥላው እየቆዩና ከጥሻ ጥሻ እየተሸጋገሩ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ወደ ሐይቁ ሄዱ፡፡ መንገዱ ብዙ ጊዜ በመፍጀቱ ግን የዚያ ሌሊት ጀልባ ታመልጣቸዋለች፡፡
ነጋባቸው፡፡ በመሆኑም ዳማሲን ወደ ቦን ቤት ረጅም መንገድ ተጉዞ ተመልሶ አደጋ ላይ መውደቅን ስላልፈለገ ንሴንጄ በሚባል በሐይቁ አካባቢ የሚኖር የእርሱና የቦን ወዳጅ ቤት ቆየ፡፡ ንሴንጄ ቤተሰባችንን የሚወድ ለዘብተኛ ሁቱ ነው፡፡ አባቴ የብዙ ወንድሞቹን የትምህርት ክፍያ በመክፈል አግዟቸዋል፡፡ ስለሆነም ዳማሲንን ለዚያን ቀን መሸሸግ በመቻሉ ደስ ተሰኘ፡፡
የንሴንጄ ወንድም ሳይመን ግን የወንድሙን ያክል ቸር አልነበረም፡፡ ዳማሲንን በቤታቸው ሲደርስ በፈገግታና በወዳጅነት ተቀብሎታል … በማግስቱ ከሰዓት በኋላ ግን ወንድሜ በተኛበትና ንሴንጄም የጀልባ ጉዞውን ለማመቻቸት በወጣበት ሳይመን ከቤት ሾልኮ ወጥቶ የገዳዮቹን ቡድን ፈልጎ ዳማሲንን አሳልፎ ሰጠው፡፡
ከእራት በፊት ሳይመን ወንድሜን ቀስቅሶ ወደ ዛየር ከመሄድህ በፊት ልብሶችህን ልጠብልህ ይለዋል፡፡ ዳማሲንም ልብሶቹን ሁሉ አወላልቆ በውስጥ ልብስ ብቻ ይቀራል፡፡ ሳይመንም ልብሶቹን ይወስድበታል፡፡ (በኋላ ላይ እንደተናገረው ይህን ያደረገው ወንድሜን ከመሞቱ በፊት ለማሳፈርና ለማሸማቀቅ ፈልጎ ነው፡፡) ልብሶቹን ከወሰደበት በኋላም ሳይመን ወንድሜን በደርዘኖች የሚቆጠሩ ገዳዮች ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ዋናው ቤት ይጠራዋል፡፡ ወንድሜም ላይ ያለ ምኅረት ተረባረቡበት፤ እየደበደቡ ወደ መንገድ ጎተቱት፡፡ ከውስጥ ልብሱም ሌላ ምንም አልለበሰም፡፡ እኛ ቤት ትሠራ የነበረች አንድ ሴት ነገሩን ሁሉ አይታ የዳማሲንን የመጨረሻ ሰዓት ዝርዝር ሁኔታ ነግራኛለች፡፡ ‹‹ቆንጆዋ እህትህ የት ነች?›› ብለው ገዳዮቹ ወንድሜን ይጠይቁታል፡፡ ‹‹የት ነች ኢማኪዩሌ?›› በቤተሰብህ ያሉትን በረሮዎች አስከሬኖች አይተናቸዋል፤ እሷ ግን ገና አልተደረሰባትም… የት ነች? ንገረንና በነጻ እንለቅሃለን፤ ካልነገርከን ግን ሌሊቱን ሙሉ ስንከትፍህ እናድራለን፡፡ በል ኢማኪዩሌ የት እንዳለች ንገረንና በነጻ ትሰናበታለህ፡፡››
ፊቱ የተሰባበረውና ያባበጠው ዳማሲን የከበቡትን ገዳዮች አየት አድርጓቸው በሕይወቴ ሙሉ እንዳደረገልኝ ሁሉ በመጨረሻዋም ቅጽበት ለኔ ቆመልኝ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሦስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ከዳማሲን_የተላከ_ደብዳቤ
፡
፡
ከትምህርት ቤቱ በስተጀርባ ብቻዬን ሆኜ የዳማሲንን ደብዳቤ ከፈትኩት፡፡ ለማንበብ የሚያስቸግረውን የእጅ ጽሑፉን እንዳየሁ በትምህርት ቤት እንዳለን የጻፈልኝን ደብዳ ቤዎች ሁሉ አስታውሼ ልቤ ታመመ፡፡ ፈጽሞ ግልጽ ስሜት የማይንጸባረቅባቸው፣ ግን ሁሌ በፍቅርና በደግነት፣ በማበረታቻና አድናቆት፣ በግሩም ምክርና ረጋ ያለ ተግሳጽ፣ ስለ ወዳጆቻችን በሚያወሱ ወሬዎችና በብዙ ቀልዶች የተሞሉ ደብዳቤዎቹ ትውስ አሉኝ፡፡ ጀርባዬን በትምህርት ቤቱ ክፍል ግድግዳ ላይ አስደግፌ ተቀምጬ አነብ ጀመር፡፡
ግንቦት 6፣ 1994
ውድ (አባባ፣ እማማ፣ ቪያኒ እና) ኢማኪዩሌ ሁላችንም ከተለያየን አንድ ወር ገደማ ሆነን፡፡ ይሄው የቅዠት ኑሮ እየኖርን ነው፡፡ ሁናቴዎች ከሚያሳዩት ነገር ባሻገር አንድ ዘውግ ሌላውን ፈጽሞ የሚያጠፋው የእግዚአብሔር ፍቃድ ሲሆን ብቻ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምናልባት የእኛ ሕይወት ለሩዋንዳ ድኅነት እንዲከፈል ግድ ብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለ አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ - እንደገና እንደምንገናኝ በአእምሮዬ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለም፡፡
ከሀገሪቱ ለመውጣት ልሞክር ነው፣ ግን ይሳካልኝ አይሳካልኝ አላውቅም፡፡ በመንገድ ላይ ከገደሉኝ ስለ እኔ አትጨነቁ፤ በሚገባ ጸልያለሁ . . . ለሞትም ተዘጋጅቻለሁ፡፡ ከሩዋንዳ መውጣት ከቻልኩ ሰላም እንደተመለሰ ወዲያውኑ ሁላችሁንም አገኛችኋለሁ፡፡ የደረሰብኝን ሁሉ ቦን
ይነግራችኋል፡፡
የዳማሲን ጓደኛ ቦን በሌላ ጊዜ እንደነገረኝ ወንድሜ ደብዳቤውን እየጻፈ ሳለ እዚህ ሐሳብ ላይ ሲደርስ ዳማሲን ብዕሩን ቁጭ አድርጎ ቀና ብሎ እያየው ‹‹ቦን፣ ወዳጄ እንደሆንክ አውቃለሁ፤ ስሜቴም ሳይጎዳ እንዲቆይ ሞክረሃል፣ አሁን ልትነግረኝ የሚገባህ ሰዓት ላይ ነን - ከቤተሰቤ አባላት የተገደለ አለ እንዴ?›› ቦን ሁቱ ስለሆነ በዘር ጭፍጨፋው ወቅት በነጻነት ይጓጓዝና በአካባቢው ከቱትሲዎች ማንኛቸው እንደተገደሉ ያውቃል፡፡ የወላጆቼንና የቪያኒን ሞት ለራሱ በምስጢር የያዘው ለወንድሜ በጣም ስለሚጠነቀቅለትና ስሜቱን ሳይጎዳ ለመጠበቅ ስለፈለገ ነው፡፡
ዳማሲን በቀጥታ ሲጠይቀው ጊዜ ቦን ከባዱን መርዶ አረዳው፡፡ ጓደኛው የሚወዳቸው የቤተሰቡ አባላት ገና በሕይወት ያሉ እየመሰለው ደብዳቤውን መጻፉን እስኪጨርስ መጠበቅን አልፈለገም፡፡ ስለዚህ ቦን ለዳማሲን አባታችን፣ እናታችንና ታናሽ ወንድማችን እንደተገደሉና እኔ ምናልባት በሕይወት ተርፌ ሊሆን እንደሚችል ይነግረዋል፡፡ ዳማሲን ቀኑን ሙሉ ማለት ይቻላል አልቅሶ እንደነበር የደብዳቤው ቋሚ ምልክት የሆኑት የእንባ ጠብታዎች ይህንን ይመሰክራሉ፡፡
ዳማሲን ኪቩ ሐይቅን ለማቋረጥ ጀልባ ፍለጋ ከመሄዱ በፊት ደብዳቤውን እንደገና አውጥቶ አባባ፣ እማማና ቪያኒ በሚሉት ቃላት ግራና ቀኝ ቅንፎችን አስቀምጦ የሚከተሉትን አረፍተ ነገሮች አከለ፡፡ ኢማኪዩሌ እንድትጠነክሪ እለምንሻለሁ፡፡ እማማ፣ አባባና ቪያኒ መገደላቸውን አሁን ሰማሁ፡፡ በተቻለኝ ፍጥነት ላገኝሽ እሞክራለሁ፡፡ ራስሽን ሳሚልኝ፤ እቀፊልኝም! በጣም የሚወድሽ ወንድምሽ!
ይህ ካነበብኳቸው ነገሮች ሁሉ የሚሠቀጥጠው ነው፡፡ እንባ ባረጠባቸው ቃላት ላይ የጣቶቼን ጫፎች አላወስኳቸውና ይህንን ደብዳቤ ሳላለቅስ ማንበብ እንደማልችል ተረዳሁ፡፡
በኋላ ላይ እንደደረስኩበት ለዘላለም የኔ ጀግና ሆኖ የሚኖረው ቦን ወንድሜን በቤቱ ከቤተሰቡ ፍላጎት በተጻራሪ ሊሸሽገው ሞክሯል፡፡ በዘር ፍጅቱ የመጀመሪያ ቀናት ዳማሲንን በምስጢር ከአልጋው ስር በደኅና በመደበቅ ሊያቆየው ችሎ ነበር፡፡ የቦን ቤተሰብ ግን ያደረገውን ነገር ሲደርስበት ዳማሲንን ለገዳዮቹ እንዲሰጥ ግፊት ያሳድርበታል፡፡
ይባስ ብሎ ቱትሲ ልጆችን በዘውግ ስም ጥሪ ወቅት ማሸማቀቅ የሚወደው ቡሆሮ ከቦን አጎቶች አንዱ ነው፡፡ ቡሆሮ በሀገሪቱ ወስጥ ካሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ውስጥ አንዱ፣ መጥፎና አደገኛ ገዳይ ሆኖ ነበርና ሲጠራጠርበት ጊዜ ቦን ዳማሲንን በጭራሽ ቤት ውስጥ ማቆየት እንደሌለበት ይረዳል፡፡ አንድ ሌሊትም በጣም አምሽቶ በቤተሰቡ መሬት ራቅ ያለ ጥግ ላይ ጉድጓድ ቆፍሮ በዕንጨትና ቅጠላቅጠል ይሸፍነዋል፡፡ ገዳዮቹ በቡሆሮ ተጠቁመው ከመምጣታቸው በፊት ዳማሲንንም በጥንቃቄ ከመኝታ ክፍሉ ያስወጣና በጉድጓዱ ውስጥ ይደብቀዋል ፡፡
ዳማሲን በጉድጓድ ውስጥ ከሦስት ሳምንታት ለበለጠ ጊዜ ያህል ተደብቆ ሳለ ገዳዮቹ በቡሆሮ ውትወታ በተደጋጋሚ የቦንን ቤት አሠሡ፡፡ እነዚህ አራጆች ግን የማይሰለቹ በመሆናቸው የቦንን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ተከታትለው መጨረሻ ላይ ምግብ ወደ ውጪ ይዞ ሲሄድ ያዩታል፡፡ ሸሻጊው ጓደኛውና ተሸሻጊው ዳማሲን ገዳዮቹ ግቢውን ሊያስሱብን ይችላሉ ብለው ሠግተው ዳማሲን የኪቩ ሐይቅን ተሻግሮ ወደ ዛየር እንዲያቀና ይወስናሉ፡፡ (ቦን የቱትሲዎችን ሕይወት ለማትረፍ ሐይቁን የሚያሻግራቸውን አንድ ደግ ሳምራዊ ዐሳ አጥማጅ ሁቱ ያውቃል፡፡) ዳማሲንን ከጉድጓዱ አውጥቶ በየጥላው እየቆዩና ከጥሻ ጥሻ እየተሸጋገሩ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ወደ ሐይቁ ሄዱ፡፡ መንገዱ ብዙ ጊዜ በመፍጀቱ ግን የዚያ ሌሊት ጀልባ ታመልጣቸዋለች፡፡
ነጋባቸው፡፡ በመሆኑም ዳማሲን ወደ ቦን ቤት ረጅም መንገድ ተጉዞ ተመልሶ አደጋ ላይ መውደቅን ስላልፈለገ ንሴንጄ በሚባል በሐይቁ አካባቢ የሚኖር የእርሱና የቦን ወዳጅ ቤት ቆየ፡፡ ንሴንጄ ቤተሰባችንን የሚወድ ለዘብተኛ ሁቱ ነው፡፡ አባቴ የብዙ ወንድሞቹን የትምህርት ክፍያ በመክፈል አግዟቸዋል፡፡ ስለሆነም ዳማሲንን ለዚያን ቀን መሸሸግ በመቻሉ ደስ ተሰኘ፡፡
የንሴንጄ ወንድም ሳይመን ግን የወንድሙን ያክል ቸር አልነበረም፡፡ ዳማሲንን በቤታቸው ሲደርስ በፈገግታና በወዳጅነት ተቀብሎታል … በማግስቱ ከሰዓት በኋላ ግን ወንድሜ በተኛበትና ንሴንጄም የጀልባ ጉዞውን ለማመቻቸት በወጣበት ሳይመን ከቤት ሾልኮ ወጥቶ የገዳዮቹን ቡድን ፈልጎ ዳማሲንን አሳልፎ ሰጠው፡፡
ከእራት በፊት ሳይመን ወንድሜን ቀስቅሶ ወደ ዛየር ከመሄድህ በፊት ልብሶችህን ልጠብልህ ይለዋል፡፡ ዳማሲንም ልብሶቹን ሁሉ አወላልቆ በውስጥ ልብስ ብቻ ይቀራል፡፡ ሳይመንም ልብሶቹን ይወስድበታል፡፡ (በኋላ ላይ እንደተናገረው ይህን ያደረገው ወንድሜን ከመሞቱ በፊት ለማሳፈርና ለማሸማቀቅ ፈልጎ ነው፡፡) ልብሶቹን ከወሰደበት በኋላም ሳይመን ወንድሜን በደርዘኖች የሚቆጠሩ ገዳዮች ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ዋናው ቤት ይጠራዋል፡፡ ወንድሜም ላይ ያለ ምኅረት ተረባረቡበት፤ እየደበደቡ ወደ መንገድ ጎተቱት፡፡ ከውስጥ ልብሱም ሌላ ምንም አልለበሰም፡፡ እኛ ቤት ትሠራ የነበረች አንድ ሴት ነገሩን ሁሉ አይታ የዳማሲንን የመጨረሻ ሰዓት ዝርዝር ሁኔታ ነግራኛለች፡፡ ‹‹ቆንጆዋ እህትህ የት ነች?›› ብለው ገዳዮቹ ወንድሜን ይጠይቁታል፡፡ ‹‹የት ነች ኢማኪዩሌ?›› በቤተሰብህ ያሉትን በረሮዎች አስከሬኖች አይተናቸዋል፤ እሷ ግን ገና አልተደረሰባትም… የት ነች? ንገረንና በነጻ እንለቅሃለን፤ ካልነገርከን ግን ሌሊቱን ሙሉ ስንከትፍህ እናድራለን፡፡ በል ኢማኪዩሌ የት እንዳለች ንገረንና በነጻ ትሰናበታለህ፡፡››
ፊቱ የተሰባበረውና ያባበጠው ዳማሲን የከበቡትን ገዳዮች አየት አድርጓቸው በሕይወቴ ሙሉ እንዳደረገልኝ ሁሉ በመጨረሻዋም ቅጽበት ለኔ ቆመልኝ
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የስደተኞች_መጠለያው_ምቾት
፡
፡
የፈረንሳዮቹ የስደተኞች መጠለያ የታጠቁ ወታደሮች የሚጠብቁት፣ ለቱትሲዎች ከለላ የሚሰጥና ሁቱዎችን የሚያገል ስፍራ ነው፡፡ ወታደሮቹ ስምንት ታንክ-መሰል ብረትለበስ ተሸከርካሪዎችን በግማሽ ክብ ቅርጽ ከትምህርት ቤቱ ሕንጻዎች ፊት ለፊት ያቆሙ ሲሆን የምሽጉን ውጨኛውን ክፍል ደግሞ ቀን ከሌት ቢያንስ መቶ የሚሆኑ ወታደሮች ይቃኙታል፡፡ እኛም ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎች ባሉበት ግማሽ ክብ ውስጥ ሙሉ ጊዜ ሰጥተው እንዲከላከሉንና መጸዳዳት ስንፈልግም ወደ ጫካ እንዲወስዱን ከተመደቡ ሰላሳ ወታደሮች ጋር እንኖራለን፡፡
የፈረንሳይ ወታደሮች በተደጋጋሚ ስለምንኖርበት ሁኔታ ይቅርታ ሲጠይቁን ያስቁኛል፡፡ ከመጣንበት ጋር ሲነጻጸር ፍጹም የምቾት ሕይወት በመኖር ላይ ነን፡፡ መጀመሪያ ላይ ከምንጭ ውሃ እናግዝና ገላችንንና ልብሳችንን በሳሙና እናጥብ ነበር!
ውጪ ላይ መተኛታችንን ፈረንሳውያኑ ወታደሮች እንደ ዋና መከራ ቢያዩትም እኛ ግን በደስታ ተቀብለነዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ በቆሻሻና በዛፍ ቅጠላ ቅጠል ተሸፍኜ በአለትና ድንጋይ ላይ በመተኛቴ የተነሳ እያመመኝ ብነሳም ክዋክብት ላይ አንጋጥጬ መተኛቱን ወድጄዋለሁ፡፡ የእግዚአብሔርን ፊት በቀኑ መጀመሪያ ላይ የማየት ያህል ነው፡፡
ምግብ እንድናዘጋጅ አይፈቀድልንም፡፡ ይህ የሆነው ትኩስ ምግብ ስላልነበራቸው ሲሆን አለማዘጋጀታችንም ለእኛ ምንም ችግር አያመጣም፡፡ ወታደሮቹ የታሸገ አይብ፣ ጣፋጭ ኮቸሮ፣ እሽግ የዱቄት ወተትና ፍራፍሬ ይመግቡናል፡፡ የምመገበው የተወሰነ ምግብ ቢሆንም ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጨመረ ሄደ፤ ወገቤም ወደ ውስጥ መግባቱን አቆመ፡፡
ፈረንሳውያን ሥራቸው እኛን መከላከል መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ይህንን ተግባራቸውንም በሚገባ ተወጥተውታል፡፡ በምሽጉ ውስጥ በቆየሁበት ወቅት አንድም ጊዜ እንኳን በገዳዮቹ ማስፈራሪያ ደርሶብኝ አያውቅም፡፡ ሆኖም ግን ሁቱዎች ብዙውን ጊዜ በውጪው የምሽጉ ክፍል በመሰብሰብ በተደረደሩት ተሸከርካሪዎች መካከል እኛን ለማየት ይሞክራሉ፡፡ በእንስሳት መጠበቂያ ያለን እንስሶች እንደሆንን ሁሉ ያፈጡብናል … ከመጥፋት ጠርዝ ድረስ የታደነ ዘውግ ብቸኛ ቅሪቶች፡፡
‹‹እንስሳት እንደሆናችሁ ሁሉ ያዩዋችኋል፣ ግን እነርሱ ናቸው እንስሶቹ›› አለኝ የወታደሮቹ አበጋዝ አንድ ቀን ጠዋት ከደረስኩ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፡፡ ፈረንሳይኛ በጥሩ ሁኔታ እንደምችል ስለተረዳ ብዙ አዋራኝ፡፡ ታሪኬን ነገርኩት፤ በጣም እንዳዘነልኝም ታየኝ፡፡ በሩዋንዳ ቱትሲዎች ያሳለፉትን፣ ታሪካችንንና የዘውግ ግጭቶችን ጣጣ ሁሉ ያውቃል፡፡
‹‹ባንቺና በኔ መካከል የሚቀር ነገር ልንገርሽ፤ የሀገሬ የርዕሰ-ብሔር ከራሱ ጋር አንዴት መታረቅ እንደሚችል አላውቅም - ጸጸቱ እንደማይገድለው›› አለኝ፡፡ ‹‹ብዙ ሁቱዎችን እንዴት ሰው እንደሚገድሉ ስላሠለጠነች ፈረንሳይ በእጆቿ ላይ ደም አለባት፡፡››
በሩዋንዳ ለተከሰተው ነገር የውጪ ዜጋ ወቀሳውን ሲቀበል ስሰማ ይህ የመጀመሪያዬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ለነፍሴ ጥሩ ነገር አደረገላት፡፡ ዓለም እየደረሰብን ያለውን ነገር አይቶ ለመርሳት መምረጡን በማወቄ የቄሱን ሬድዮ ስሰማ ብዙ ጊዜ ተስፋ እቆርጥ ነበር፡፡
‹‹ይህን ያህል ስለተረዳኸኝ አመሰግናለሁ›› ስል መለስኩለት፡፡ ‹‹ይህን እያደረጉ ያሉት ሰዎች በጣም መጥፎዎች ናቸው፡፡
‹‹መጥፎ? መጥፎ! ኢማኪዩሌ ከንቱ ግፈኞች ናቸው፡፡ ጭራቆች ናቸው! በደኅና ሁናቴ ላይ እንዳለሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ፡፡ እኔ እዚህ በሥራ ላይ እያለሁ አንዳች ጉዳት አይመጣብሽም›› አለኝ በወገቡ ላይ ያገነደረውን ጠመንጃ መታ መታ እያደረገ፡፡ ‹‹ላንቺ ከመከላከልም በላይ አደርግልሻለሁ፡፡ የተወሰነ ፍትሕም እለግስሻለሁ፡፡ አሁንም ይህ በኔና ባንቺ መካከል ይቅር እንጂ በቀል ከፈለግሽ ያንቺው ድርሻ ነው፡፡ ይፈልጉሽ የነበሩትን ወይንም ወላጆችሽንና ወንድሞችሽን የገደሉትን ሁቱዎች ስሞች ብትሰጭኝ አስገድልልሻለሁ፡፡
ያቀረበው ሐሳብ አስደነገጠኝ፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ በነበርኩባቸው የመጀመሪያ ቀናት ሰሞን የተመኘሁት ይህንኑ ነበር፡፡ በኛ ሰዎች ላይ እየተፈጸሙ የነበሩትን ግድያዎች ቄሱ በነገሩን ጊዜ በቀልን በጽኑ በመፈለጌ ሁቱዎችን የምገድልበት ጠመንጃና መድፍ ቢኖረኝ ተመኝቼ ነበር፡፡ ያ ግን ልቤን ለእግዚአብሔር ምኅረት ከመክፈቴና ከገዳዮቹ ጋር ሰላም ከመፍጠሬ በፊት ነው፡፡
መኰንኑ ያቀረበልኝ ትክክለኛውን በቀል ነው - በኔ ትዕዛዝ የሚገድሉ የሠለጠኑና የታጠቁ ወታደሮችን፡፡ ማድረግ የሚጠበቅብኝ ብቸኛው ነገር አንድ ስም ሹክ ማለትና የቤተሰቤንና በሺዎች የሚቆጠሩትን በየጎዳናው እየበሰበሱ የነበሩትን ሰዎች ደም መበቀል ነው፡፡ በቀሉ ከልቡ የመጣ ቢሆንም በመኰንኑ ድምጽ ውስጥ ዲያብሎስ ይሰማኛል፡፡ በወቅቱ የምፈልገው ብቸኛ ነገር ሰላም ሆኖ ሳለ ይህ መኰንን በግድያ ቃል ኪዳኖች ይፈታተነኛል፡፡ እጄን ወደ ኪሴ አስገብቼ በአባቴ መቁጠሪያ
ጠቀለልኩት፡፡ ‹‹ይህን አደርግልሻለሁ በማለትህ አመሰግናለሁ -››
‹‹የምትፈልጊውን እገድልለሻለሁ!›› ለመግደል በጣም ከመጓጓቱ የተነሣ ንግግሬን እንኳን አላስጨርስ አለኝ፡፡ ‹‹በዚህ ምሽግ የምታውቂው ሁቱ ካለ ንገሪኝና እኔ ራሴ እገድለዋለሁ፡፡ ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፡፡››
‹‹አዎን፣ እነዚህ ገዳዮች እንጂ ሁቱዎች ሁሉ ከንቱ አይደሉም መኰንን ሆይ፡፡ በዲያብሎስ ተታለዋል… ከአምላክ ርቀው ሄደዋል እና -››
‹‹ኢማኪዩሌ ሁቱዎች ከንቱ ናቸው›› እንደገና አቋረጠኝ፡፡ ‹‹ያደረጉት ከንቱ ነው፡፡ ይህ የጌታ ፈቃድ አሊያም የዲያብሎስ ሥራ እንደሆነ አትንገሪኝ - የሁቱዎች ሥራ ነው፡፡ እናም ብድራቸውን ያገኟታል፡፡ ሐሳብሽን ከቀየርሽ አሳውቂኝ፡፡ ለሌላ ሰው እኮ ልግደል አልልም፤ ታውቂያለሽ፡፡››
አምላክ የመኰንኑን ልብ በምህረቱ እንዲነካ ጸልዬ ለገዳዮቹም እንደገና ገጀራዎቻቸውን እንዲጥሉና የእግዚአብሔርን ምኅረት እንዲለምኑ ጸለይኩ፡፡ የመኰንኑ ንዴት በሩዋንዳ የጥላቻና ያለመተማመኑ ዑደት በቀላሉ እንደማይሰበር እንዳስብ አደረገኝ፡፡ እንዲያውም ግድያው ካቆመም በኋላ በእርግጠኝነት የባሰ መራር ሁኔታ ሊኖር ይችላል፤ ወደ ባሰ ሽብር የሚፈነዳ መራርነት፡፡ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ምኅረት ብቻ ያንን አሁን ከመከሰት ያቆመው ይሆናል፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ አምላክ ቢያስቀምጠኝ ያንን ማየት እችላለሁ - ሌሎች እንዲኖሩ ማድረግም የሕይወቴ ሥራ ዋነኛ ክፍል ይሆናል፡፡
በቀጣዩ ቀን መኰንኑ ቃሉን መጠበቁን አሳየ - ሁቱዎችን በእውነት ይጠላ ኖሯል፡፡ አንድ እየደማ ያለና ‹‹የዘር ጭፍጨፋ ተራፊ ነኝ፤ የቆሰልኩትም ከቱትሲ አማጽያን ጎን ስዋጋ ነው›› የሚል ሰው ወደ ምሽጉ ገብቶ ይዘዋወራል፡፡ መኰንኑ ግን ስላላመነው ወታደሮቹ አንበርክከውና ጠመንጃዎቻቸውን ራሱ ላይ ደግነው እንዲጠይቁት አደረገ፡፡ መጀመሪያ ላይ ሲጠይቁት የኢንተርሃምዌ አባል መሆኑን ካደ፡፡ ከብዙ ምርመራ በኋላ ግን ተስፋ ቆረጠና ተናዘዘ፡፡ መኰንኑም ለወታደሮቹ ራሱን ሲነቀንቅላቸው ጎትተው ወሰዱት፤ ከዚያ በኋላም በጭራሽ አላየነውም፡፡ ከወታደሮቹ አንደኛው በሌላ ጊዜ ሰውዬው የኢንተርሃምዌ ሰላይ እንደሆነ ማመኑን ነገረኝ፡፡
‹‹ስለሱ አትጨነቂ - ከአሁን በኋላ አያስቸግርሽም›› አለኝ፡፡
ለአክስቶቼና ለልጆቻቸው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የስደተኞች_መጠለያው_ምቾት
፡
፡
የፈረንሳዮቹ የስደተኞች መጠለያ የታጠቁ ወታደሮች የሚጠብቁት፣ ለቱትሲዎች ከለላ የሚሰጥና ሁቱዎችን የሚያገል ስፍራ ነው፡፡ ወታደሮቹ ስምንት ታንክ-መሰል ብረትለበስ ተሸከርካሪዎችን በግማሽ ክብ ቅርጽ ከትምህርት ቤቱ ሕንጻዎች ፊት ለፊት ያቆሙ ሲሆን የምሽጉን ውጨኛውን ክፍል ደግሞ ቀን ከሌት ቢያንስ መቶ የሚሆኑ ወታደሮች ይቃኙታል፡፡ እኛም ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎች ባሉበት ግማሽ ክብ ውስጥ ሙሉ ጊዜ ሰጥተው እንዲከላከሉንና መጸዳዳት ስንፈልግም ወደ ጫካ እንዲወስዱን ከተመደቡ ሰላሳ ወታደሮች ጋር እንኖራለን፡፡
የፈረንሳይ ወታደሮች በተደጋጋሚ ስለምንኖርበት ሁኔታ ይቅርታ ሲጠይቁን ያስቁኛል፡፡ ከመጣንበት ጋር ሲነጻጸር ፍጹም የምቾት ሕይወት በመኖር ላይ ነን፡፡ መጀመሪያ ላይ ከምንጭ ውሃ እናግዝና ገላችንንና ልብሳችንን በሳሙና እናጥብ ነበር!
ውጪ ላይ መተኛታችንን ፈረንሳውያኑ ወታደሮች እንደ ዋና መከራ ቢያዩትም እኛ ግን በደስታ ተቀብለነዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ በቆሻሻና በዛፍ ቅጠላ ቅጠል ተሸፍኜ በአለትና ድንጋይ ላይ በመተኛቴ የተነሳ እያመመኝ ብነሳም ክዋክብት ላይ አንጋጥጬ መተኛቱን ወድጄዋለሁ፡፡ የእግዚአብሔርን ፊት በቀኑ መጀመሪያ ላይ የማየት ያህል ነው፡፡
ምግብ እንድናዘጋጅ አይፈቀድልንም፡፡ ይህ የሆነው ትኩስ ምግብ ስላልነበራቸው ሲሆን አለማዘጋጀታችንም ለእኛ ምንም ችግር አያመጣም፡፡ ወታደሮቹ የታሸገ አይብ፣ ጣፋጭ ኮቸሮ፣ እሽግ የዱቄት ወተትና ፍራፍሬ ይመግቡናል፡፡ የምመገበው የተወሰነ ምግብ ቢሆንም ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጨመረ ሄደ፤ ወገቤም ወደ ውስጥ መግባቱን አቆመ፡፡
ፈረንሳውያን ሥራቸው እኛን መከላከል መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ይህንን ተግባራቸውንም በሚገባ ተወጥተውታል፡፡ በምሽጉ ውስጥ በቆየሁበት ወቅት አንድም ጊዜ እንኳን በገዳዮቹ ማስፈራሪያ ደርሶብኝ አያውቅም፡፡ ሆኖም ግን ሁቱዎች ብዙውን ጊዜ በውጪው የምሽጉ ክፍል በመሰብሰብ በተደረደሩት ተሸከርካሪዎች መካከል እኛን ለማየት ይሞክራሉ፡፡ በእንስሳት መጠበቂያ ያለን እንስሶች እንደሆንን ሁሉ ያፈጡብናል … ከመጥፋት ጠርዝ ድረስ የታደነ ዘውግ ብቸኛ ቅሪቶች፡፡
‹‹እንስሳት እንደሆናችሁ ሁሉ ያዩዋችኋል፣ ግን እነርሱ ናቸው እንስሶቹ›› አለኝ የወታደሮቹ አበጋዝ አንድ ቀን ጠዋት ከደረስኩ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፡፡ ፈረንሳይኛ በጥሩ ሁኔታ እንደምችል ስለተረዳ ብዙ አዋራኝ፡፡ ታሪኬን ነገርኩት፤ በጣም እንዳዘነልኝም ታየኝ፡፡ በሩዋንዳ ቱትሲዎች ያሳለፉትን፣ ታሪካችንንና የዘውግ ግጭቶችን ጣጣ ሁሉ ያውቃል፡፡
‹‹ባንቺና በኔ መካከል የሚቀር ነገር ልንገርሽ፤ የሀገሬ የርዕሰ-ብሔር ከራሱ ጋር አንዴት መታረቅ እንደሚችል አላውቅም - ጸጸቱ እንደማይገድለው›› አለኝ፡፡ ‹‹ብዙ ሁቱዎችን እንዴት ሰው እንደሚገድሉ ስላሠለጠነች ፈረንሳይ በእጆቿ ላይ ደም አለባት፡፡››
በሩዋንዳ ለተከሰተው ነገር የውጪ ዜጋ ወቀሳውን ሲቀበል ስሰማ ይህ የመጀመሪያዬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ለነፍሴ ጥሩ ነገር አደረገላት፡፡ ዓለም እየደረሰብን ያለውን ነገር አይቶ ለመርሳት መምረጡን በማወቄ የቄሱን ሬድዮ ስሰማ ብዙ ጊዜ ተስፋ እቆርጥ ነበር፡፡
‹‹ይህን ያህል ስለተረዳኸኝ አመሰግናለሁ›› ስል መለስኩለት፡፡ ‹‹ይህን እያደረጉ ያሉት ሰዎች በጣም መጥፎዎች ናቸው፡፡
‹‹መጥፎ? መጥፎ! ኢማኪዩሌ ከንቱ ግፈኞች ናቸው፡፡ ጭራቆች ናቸው! በደኅና ሁናቴ ላይ እንዳለሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ፡፡ እኔ እዚህ በሥራ ላይ እያለሁ አንዳች ጉዳት አይመጣብሽም›› አለኝ በወገቡ ላይ ያገነደረውን ጠመንጃ መታ መታ እያደረገ፡፡ ‹‹ላንቺ ከመከላከልም በላይ አደርግልሻለሁ፡፡ የተወሰነ ፍትሕም እለግስሻለሁ፡፡ አሁንም ይህ በኔና ባንቺ መካከል ይቅር እንጂ በቀል ከፈለግሽ ያንቺው ድርሻ ነው፡፡ ይፈልጉሽ የነበሩትን ወይንም ወላጆችሽንና ወንድሞችሽን የገደሉትን ሁቱዎች ስሞች ብትሰጭኝ አስገድልልሻለሁ፡፡
ያቀረበው ሐሳብ አስደነገጠኝ፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ በነበርኩባቸው የመጀመሪያ ቀናት ሰሞን የተመኘሁት ይህንኑ ነበር፡፡ በኛ ሰዎች ላይ እየተፈጸሙ የነበሩትን ግድያዎች ቄሱ በነገሩን ጊዜ በቀልን በጽኑ በመፈለጌ ሁቱዎችን የምገድልበት ጠመንጃና መድፍ ቢኖረኝ ተመኝቼ ነበር፡፡ ያ ግን ልቤን ለእግዚአብሔር ምኅረት ከመክፈቴና ከገዳዮቹ ጋር ሰላም ከመፍጠሬ በፊት ነው፡፡
መኰንኑ ያቀረበልኝ ትክክለኛውን በቀል ነው - በኔ ትዕዛዝ የሚገድሉ የሠለጠኑና የታጠቁ ወታደሮችን፡፡ ማድረግ የሚጠበቅብኝ ብቸኛው ነገር አንድ ስም ሹክ ማለትና የቤተሰቤንና በሺዎች የሚቆጠሩትን በየጎዳናው እየበሰበሱ የነበሩትን ሰዎች ደም መበቀል ነው፡፡ በቀሉ ከልቡ የመጣ ቢሆንም በመኰንኑ ድምጽ ውስጥ ዲያብሎስ ይሰማኛል፡፡ በወቅቱ የምፈልገው ብቸኛ ነገር ሰላም ሆኖ ሳለ ይህ መኰንን በግድያ ቃል ኪዳኖች ይፈታተነኛል፡፡ እጄን ወደ ኪሴ አስገብቼ በአባቴ መቁጠሪያ
ጠቀለልኩት፡፡ ‹‹ይህን አደርግልሻለሁ በማለትህ አመሰግናለሁ -››
‹‹የምትፈልጊውን እገድልለሻለሁ!›› ለመግደል በጣም ከመጓጓቱ የተነሣ ንግግሬን እንኳን አላስጨርስ አለኝ፡፡ ‹‹በዚህ ምሽግ የምታውቂው ሁቱ ካለ ንገሪኝና እኔ ራሴ እገድለዋለሁ፡፡ ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፡፡››
‹‹አዎን፣ እነዚህ ገዳዮች እንጂ ሁቱዎች ሁሉ ከንቱ አይደሉም መኰንን ሆይ፡፡ በዲያብሎስ ተታለዋል… ከአምላክ ርቀው ሄደዋል እና -››
‹‹ኢማኪዩሌ ሁቱዎች ከንቱ ናቸው›› እንደገና አቋረጠኝ፡፡ ‹‹ያደረጉት ከንቱ ነው፡፡ ይህ የጌታ ፈቃድ አሊያም የዲያብሎስ ሥራ እንደሆነ አትንገሪኝ - የሁቱዎች ሥራ ነው፡፡ እናም ብድራቸውን ያገኟታል፡፡ ሐሳብሽን ከቀየርሽ አሳውቂኝ፡፡ ለሌላ ሰው እኮ ልግደል አልልም፤ ታውቂያለሽ፡፡››
አምላክ የመኰንኑን ልብ በምህረቱ እንዲነካ ጸልዬ ለገዳዮቹም እንደገና ገጀራዎቻቸውን እንዲጥሉና የእግዚአብሔርን ምኅረት እንዲለምኑ ጸለይኩ፡፡ የመኰንኑ ንዴት በሩዋንዳ የጥላቻና ያለመተማመኑ ዑደት በቀላሉ እንደማይሰበር እንዳስብ አደረገኝ፡፡ እንዲያውም ግድያው ካቆመም በኋላ በእርግጠኝነት የባሰ መራር ሁኔታ ሊኖር ይችላል፤ ወደ ባሰ ሽብር የሚፈነዳ መራርነት፡፡ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ምኅረት ብቻ ያንን አሁን ከመከሰት ያቆመው ይሆናል፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ አምላክ ቢያስቀምጠኝ ያንን ማየት እችላለሁ - ሌሎች እንዲኖሩ ማድረግም የሕይወቴ ሥራ ዋነኛ ክፍል ይሆናል፡፡
በቀጣዩ ቀን መኰንኑ ቃሉን መጠበቁን አሳየ - ሁቱዎችን በእውነት ይጠላ ኖሯል፡፡ አንድ እየደማ ያለና ‹‹የዘር ጭፍጨፋ ተራፊ ነኝ፤ የቆሰልኩትም ከቱትሲ አማጽያን ጎን ስዋጋ ነው›› የሚል ሰው ወደ ምሽጉ ገብቶ ይዘዋወራል፡፡ መኰንኑ ግን ስላላመነው ወታደሮቹ አንበርክከውና ጠመንጃዎቻቸውን ራሱ ላይ ደግነው እንዲጠይቁት አደረገ፡፡ መጀመሪያ ላይ ሲጠይቁት የኢንተርሃምዌ አባል መሆኑን ካደ፡፡ ከብዙ ምርመራ በኋላ ግን ተስፋ ቆረጠና ተናዘዘ፡፡ መኰንኑም ለወታደሮቹ ራሱን ሲነቀንቅላቸው ጎትተው ወሰዱት፤ ከዚያ በኋላም በጭራሽ አላየነውም፡፡ ከወታደሮቹ አንደኛው በሌላ ጊዜ ሰውዬው የኢንተርሃምዌ ሰላይ እንደሆነ ማመኑን ነገረኝ፡፡
‹‹ስለሱ አትጨነቂ - ከአሁን በኋላ አያስቸግርሽም›› አለኝ፡፡
ለአክስቶቼና ለልጆቻቸው
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_አማጽያኑ_የሚወስደው_መንገድ
፡
፡
በነሃሴ መጨረሻ በአንድ ሞቃት ከሰዓት በኋላ የፈረንሳዩ መኰንን ምሽጉን ለቀን ልንሄድ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ ዘመቻ ቱርኮይዝ ተጠናቀቀ፣ ስለሆነም ፈረንሳውያኑ ከሩዋንዳ ለመውጣት ይዘገጃጃሉ፡፡ ‹‹ምሽጋችንን ዛሬ እንዘጋለን›› አለኝ፡፡ ‹‹በሁለት ሰዓታት ውስጥ ሁሉም ሰው ይህን ምሽግ ለቆ እንዲወጣ ይዘገጃጅ፡፡››
‹‹የት ነው የምንሄደው?›› ስል ጠየቅሁት፡፡ ‹‹እዚህ ሰላሳ ሰዎች አሉ… የት ሂዱ ልበላቸው? ቤት የለንም!›› በድንገተኛው ዜና ተገረምኩ፡፡
‹‹ሁላችሁንም ከቱትሲ ወታደሮች ጋር እንድትቆዩ ልንወስዳችሁ ነው፡፡ ሩአግ ወደ አካባቢው የተጠጋ ሲሆን ካለንበት ስፍራ የተወሰኑ ኪሎሜትሮች ራቅ ብሎም ምሽግ
አቋቁሟል፡፡ እዚያ ወስደን ለእነርሱ እንሰጣችኋለን፡፡ ከራሳችሁ ሰዎች ጋር መሆኑ ይሻላችኋል፡፡››
የቱትሲ ወታደሮቹ በመጨረሻ ወደኛ እየተዋጉ መምጣታቸውንና ኢንተርሃምዌዎችን ከሀገር እያስወጡ መሆናቸውን በመስማቴ ተደሰትኩ፡፡ ጀግናችን፣ የሩአጉ መሪ ፖል ካጋሜ፣ በኪጋሊ አዲስ መንግሥት ማቋቋሙን ሳይቀር ሰማሁ፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን በመጨረሻም ሰላም አገኘን - ያች ቀን ደረሰች፤ የዘር ጭፍጨፋው መቆሙ ነው!
መሄዳችን መሆኑን በምሽጉ እየተዘዋወርኩ ለእያንዳንዱ ሰው ተናገርኩ፡፡ በቅርቡ ከመጡት አንዳንዶቹ ተጠራጠሩ፤ ፈረንሳውያኑ የማይታመኑና የስደተኛ መጠለያውን ያዘጋጁትም የዘር ጭፍጨፋውን ያስተባበሩትን ሁቱዎች በኪቩ ሐይቅ የማሻገርና ከሩዋንዳ በደኅና የማስወጣት እውነተኛ ተልዕኳቸውን ለመሸፈን እንደ ሰብዓዊ መከላከያ አድርገው ለመጠቀም ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡
‹‹ይህን እንኳን አላምንም›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ለሳምንታት በደኅና ይዘውን ከርመዋል፤ ነጻ ሊያወጡንም ትንሽ ነው የቀራቸው! እናደርጋለን ያሉትን ሁሉ እያደረጉልን ነው፡፡››
በተጠንቀቅ ስለሆንን ለመዘገጃጀት ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ ጓዝ ብሎ ነገር ያለው ስደተኛ የለም፡፡ በመሆኑም የምንሸክፈው ኮተት የለንም፡፡ ያሉኝን ጥቂት ንብረቶች ሰባሰብኩ - የቄስ ሙሪንዚ ልጅ የሰጠችኝን ሹራቤንና ፎጣዬን፣ ፒየር የሰጠኝን ሁለት መጻሕፍትና የተወሰኑ ወታደሮቹ የሰጡኝን ትርፍ ሳሙናዎችና ቲሸርቶችን በከረጢት አደረግሁ፡፡ ይህን ሳደርግ ግን እናቴ ገዳዮቹ በቤታችን አካባቢ እንደተሰበሰቡ እቃዎቿን በሻንጣዎች ስትከት የነበረው ትዝ አለኝና ካለፈው ሕይወቴ እቃዎችን ወደ አዲሱ ሕይወቴ ማንኳተት እንደሌለብኝ ወሰንኩ፡፡ በሁለቱ ሕይወቶቼ መካከል ንጹሕ መለያያ ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ከረጢቱን አንድ ሌላ ምስኪን ቤት-አልባ ቱትሲ ያገኘው ዘንድ በመመኘት ወደ መማሪያ ክፍሉ ወስጄ ጥጋት ላይ ተውኩት፡፡ ልሄድ ዘወር ስል በሩ ላይ ከቆመው ከፒየር ጋር ድንገት ግጥምጥም አልን፡፡ በሐዘኔታ አየኝና አንዲት ወረቀት ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንዲያው ምናልባት ሐሳብሽን ከቀየርሽ ይህ የፈረንሳዩ አድራሻዬ ነው፡፡ በጣም እናፍቅሻለሁ፤ በልቤም አኖርሻለሁ፡፡ አምላክ በደኅና እንዲያቆይሽ እጸልያለሁ፡፡››
‹‹በል ደኅና ሁን ፒየር፡፡ እግዚአብሔር ይባርክህ›› ብልም እርሱ ግን ምላሼን እንኳን ሳይሰማ ሄዶ ኖሯል፡፡
በተሸከርካሪው ኋላ ላይ ለመውጣት የመጨረሻዋ ነኝ፡፡ የኋላ መዝጊያው ገጭ ብሎ ሲዘጋ የሸራ ከለላው እኛን ለመደበቅ ቁልቁል ተጋረደ፤ ተሽከርካሪውም ወደፊት ተንቀሳቀሰ፡፡ መቼም አሳልፌ የማልሰጠው ንብረቴን፣ አባቴ የሰጠኝን መቁጠሪያዬን፣ አወጣሁና ጸሎቴን አደረስኩበት፡፡ እግዚአብሔርን በአዲሱ መንገዳችን እንዲባርከንና ወደ ቱትሲ ወታደሮቹ በደኅና እንዲያደርሰን ጠየቅሁት፡፡
ተሸከርካሪው በግማሽ ክብ ቅርጽ የተደረደሩትን ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችና ቁልቁል ጥርጊያ መንገዱን አልፎ ወደ ገዳዮች ባሕር ሰጠመ! ሸራው ላይ ባለች ትንሽ ቀዳዳ አጮልቄ በሺዎች የሚቆጠሩ ሁቱዎች በዋናው መንገድ ወደ ኪቩ ሐይቅ ሲተሙ አየሁ - ከመካከላቸው በመቶዎች የሚቆጠሩት የኢንተርሃምዌን የደንብ ልብስ ለብሰው ገጀራ ይዘዋል፡፡
‹‹ወይ አምላኬ›› አልኩ ተሸከርካሪው ላይ እንደገና ወድቄ፡፡ ‹‹ድጋሚ አያምጣው!›› ሁቱዎቹ መንገድ እንዲለቁና እንዲያሳልፉን የተሸከርካሪውን ጡሩንባ እየነፋን በተጨናነቀው መንገድ እናዘግም ገባን፡፡ ኢንተርሃምዌዎቹ ካስቆሙን ወይም ተሸከርካሪያችን ከተበላሸ በደቂቃዎች ውስጥ ይረባረቡብናል፡፡ መታጠቢያ ቤቱን ለቅቄ ከወጣሁ ወዲህ ይህን ያህል ፈርቼ አላውቅም፡፡
‹‹እባክህ አምላኬ›› ስል ጸለይኩ፡፡ ‹‹ይህን ያህል አምጥተኸናል - አሁን ቀሪውንም ጎዳና ውሰደን! እነዚህን ገዳዮችም አሳውርልን … እዚህ ተሸከርካሪ ጀርባ ላይ እንዲያዩ አታድርጋቸው፡፡ መሐሪው ጌታ ሆይ! ከነዚህ ጥላቻ ከተሞላባቸው ዓይኖቻቸው ሰውረን!››
ወደ ሩአግ ምሽግ ከሚወስደን መንገዳችን ከግማሽ በላይ እንደሄድን ተሸከርካሪው ቆመ፡፡ ፈረንሳዊው መኰንን ወደ ኋላ መጥቶ ሸራውን ገለጠና ‹‹በአካባቢው ተኩስ አለ የሚል ወሬ ደርሶናል፤ ስለሆነም በማናቸውም ሁኔታ ቢሆን ተኩስን የማስቆም ግዴታ አለብን፡፡ ስለዚህ ልንመለስ ስለሆነ የግድ እዚህ መውረድ አለባችሁ፡፡›› አሳስቼ የሰማሁት መሰለኝ፡፡ ‹‹መልሰህ ትወስደናለህ ማለት ነው፣ አይደል?››
‹‹አይ፣ መጠለያውን ልንዘጋው ስለሆነ ብትመለሱም የምታርፉበት ስፍራ የለም፡፡ እዚህ መውረድ አለባችሁ… አሁኑኑ፡፡ ይቅርታ እንግዲህ ኢማኪዩሌ፡፡›› ባለፉት ጥቂት ሳምንታት መኰንኑን በደንብ አውቄዋለሁ፡፡ ሁቱ ገዳዮችን ስለሚጠላ ቱትሲዎችን በተቻለው መጠን ለመርዳት እንደሚፈልግ ተናግሯል፤ ስለሆነም በታጠቁ ኢንተርሃምዌዎች እጅ ሊጥለን ነው ብዬ ላምን አልቻልኩም፡፡ እርሱን ለማሳመን ከተሽከርካሪው ወረድኩ፡፡ ‹‹እባክህ፣ መኰንን ሆይ፣ እዚህ ከተውከን ምን እንደሚከሰትብን ከማንም በላይ ታውቃለህ፡፡ በዙሪያችን ገዳዮቹ እያንዣበቡ ነው! እባክህ ተለመነኝ … የሩአግ ምሽግ ከዚህ በኋላ ግፋ ቢል አንድ ኪሎሜትር ስለሚርቅ እባክህ እዚያ አድርሰን፤ አሊያም መልሰህ ውሰደን … እዚህ ለእርድ አትተወን!››
‹‹ይቅርታ ኢማኪዩሌ፡፡ ትዕዛዝ አለብኝ፡፡››
‹‹እባክህ መኰንን ብትወስደን ምናለ!››
‹‹አይ! ሰዎችሽን አውርጅልኝ፡፡ መሄድ አለብን፡፡››
አንድ ደርዘን ገደማ ኢንተርሃምዌዎች አሥር ጫማ በሚሆን ርቀት እየተከታተሉን፣ የምንነጋገረውን እየሰሙና ፍላጎታቸው በጣም አይሎ ስለቆሙ እየተከሰተ ያለውን ነገር ልናምን አልቻልንም፡፡ ጨነቀኝ፤ መሬቷም ዞረችብኝ፣ ለአንድ አፍታ እንኳን የማየው ነገር የቁጡ ፊቶችን ብዥታ ሆነ፡፡ ራሴን በተሸከርካሪው አንድ ጎን ላይ አረጋግቼ ቆሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በመሬት ላይ ያሉትን አስከሬኖች ምንነት አወቅሁ - መንገዱን ተከትሎ ዓይኔ እስከሚያየው ድረስ ሳማትር አስከሬኖች በየቦታው ወድቀዋል፡፡
መኰንኑን ቀና ብዬ አይቼ በዓይኖቼ ለመጨረሻ ጊዜ ተለማመጥኩት፡፡ ረብ-አልባ ነው - ወይ ፍንክች አለ፡፡ ምናልባት ቄሱና ሌሎቹ ስለ ፈረንሳውያኑ የተናገሩት ልክ ነው ማለት ነው፡፡ እውነት እዚህ የመጡት ገዳዮቹን ለመርዳት ይሆን? ይኸው በእርግጠኝነት ለሞት ሊተዉን ነው፡፡
ለጓደኞቼ ‹‹ኑ ውረዱ›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ሁላችሁም ውረዱ … ፈረንጆቹ እዚህ ትተውን ሊሄዱ ነው፡፡››
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_አማጽያኑ_የሚወስደው_መንገድ
፡
፡
በነሃሴ መጨረሻ በአንድ ሞቃት ከሰዓት በኋላ የፈረንሳዩ መኰንን ምሽጉን ለቀን ልንሄድ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ ዘመቻ ቱርኮይዝ ተጠናቀቀ፣ ስለሆነም ፈረንሳውያኑ ከሩዋንዳ ለመውጣት ይዘገጃጃሉ፡፡ ‹‹ምሽጋችንን ዛሬ እንዘጋለን›› አለኝ፡፡ ‹‹በሁለት ሰዓታት ውስጥ ሁሉም ሰው ይህን ምሽግ ለቆ እንዲወጣ ይዘገጃጅ፡፡››
‹‹የት ነው የምንሄደው?›› ስል ጠየቅሁት፡፡ ‹‹እዚህ ሰላሳ ሰዎች አሉ… የት ሂዱ ልበላቸው? ቤት የለንም!›› በድንገተኛው ዜና ተገረምኩ፡፡
‹‹ሁላችሁንም ከቱትሲ ወታደሮች ጋር እንድትቆዩ ልንወስዳችሁ ነው፡፡ ሩአግ ወደ አካባቢው የተጠጋ ሲሆን ካለንበት ስፍራ የተወሰኑ ኪሎሜትሮች ራቅ ብሎም ምሽግ
አቋቁሟል፡፡ እዚያ ወስደን ለእነርሱ እንሰጣችኋለን፡፡ ከራሳችሁ ሰዎች ጋር መሆኑ ይሻላችኋል፡፡››
የቱትሲ ወታደሮቹ በመጨረሻ ወደኛ እየተዋጉ መምጣታቸውንና ኢንተርሃምዌዎችን ከሀገር እያስወጡ መሆናቸውን በመስማቴ ተደሰትኩ፡፡ ጀግናችን፣ የሩአጉ መሪ ፖል ካጋሜ፣ በኪጋሊ አዲስ መንግሥት ማቋቋሙን ሳይቀር ሰማሁ፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን በመጨረሻም ሰላም አገኘን - ያች ቀን ደረሰች፤ የዘር ጭፍጨፋው መቆሙ ነው!
መሄዳችን መሆኑን በምሽጉ እየተዘዋወርኩ ለእያንዳንዱ ሰው ተናገርኩ፡፡ በቅርቡ ከመጡት አንዳንዶቹ ተጠራጠሩ፤ ፈረንሳውያኑ የማይታመኑና የስደተኛ መጠለያውን ያዘጋጁትም የዘር ጭፍጨፋውን ያስተባበሩትን ሁቱዎች በኪቩ ሐይቅ የማሻገርና ከሩዋንዳ በደኅና የማስወጣት እውነተኛ ተልዕኳቸውን ለመሸፈን እንደ ሰብዓዊ መከላከያ አድርገው ለመጠቀም ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡
‹‹ይህን እንኳን አላምንም›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ለሳምንታት በደኅና ይዘውን ከርመዋል፤ ነጻ ሊያወጡንም ትንሽ ነው የቀራቸው! እናደርጋለን ያሉትን ሁሉ እያደረጉልን ነው፡፡››
በተጠንቀቅ ስለሆንን ለመዘገጃጀት ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ ጓዝ ብሎ ነገር ያለው ስደተኛ የለም፡፡ በመሆኑም የምንሸክፈው ኮተት የለንም፡፡ ያሉኝን ጥቂት ንብረቶች ሰባሰብኩ - የቄስ ሙሪንዚ ልጅ የሰጠችኝን ሹራቤንና ፎጣዬን፣ ፒየር የሰጠኝን ሁለት መጻሕፍትና የተወሰኑ ወታደሮቹ የሰጡኝን ትርፍ ሳሙናዎችና ቲሸርቶችን በከረጢት አደረግሁ፡፡ ይህን ሳደርግ ግን እናቴ ገዳዮቹ በቤታችን አካባቢ እንደተሰበሰቡ እቃዎቿን በሻንጣዎች ስትከት የነበረው ትዝ አለኝና ካለፈው ሕይወቴ እቃዎችን ወደ አዲሱ ሕይወቴ ማንኳተት እንደሌለብኝ ወሰንኩ፡፡ በሁለቱ ሕይወቶቼ መካከል ንጹሕ መለያያ ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ከረጢቱን አንድ ሌላ ምስኪን ቤት-አልባ ቱትሲ ያገኘው ዘንድ በመመኘት ወደ መማሪያ ክፍሉ ወስጄ ጥጋት ላይ ተውኩት፡፡ ልሄድ ዘወር ስል በሩ ላይ ከቆመው ከፒየር ጋር ድንገት ግጥምጥም አልን፡፡ በሐዘኔታ አየኝና አንዲት ወረቀት ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንዲያው ምናልባት ሐሳብሽን ከቀየርሽ ይህ የፈረንሳዩ አድራሻዬ ነው፡፡ በጣም እናፍቅሻለሁ፤ በልቤም አኖርሻለሁ፡፡ አምላክ በደኅና እንዲያቆይሽ እጸልያለሁ፡፡››
‹‹በል ደኅና ሁን ፒየር፡፡ እግዚአብሔር ይባርክህ›› ብልም እርሱ ግን ምላሼን እንኳን ሳይሰማ ሄዶ ኖሯል፡፡
በተሸከርካሪው ኋላ ላይ ለመውጣት የመጨረሻዋ ነኝ፡፡ የኋላ መዝጊያው ገጭ ብሎ ሲዘጋ የሸራ ከለላው እኛን ለመደበቅ ቁልቁል ተጋረደ፤ ተሽከርካሪውም ወደፊት ተንቀሳቀሰ፡፡ መቼም አሳልፌ የማልሰጠው ንብረቴን፣ አባቴ የሰጠኝን መቁጠሪያዬን፣ አወጣሁና ጸሎቴን አደረስኩበት፡፡ እግዚአብሔርን በአዲሱ መንገዳችን እንዲባርከንና ወደ ቱትሲ ወታደሮቹ በደኅና እንዲያደርሰን ጠየቅሁት፡፡
ተሸከርካሪው በግማሽ ክብ ቅርጽ የተደረደሩትን ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችና ቁልቁል ጥርጊያ መንገዱን አልፎ ወደ ገዳዮች ባሕር ሰጠመ! ሸራው ላይ ባለች ትንሽ ቀዳዳ አጮልቄ በሺዎች የሚቆጠሩ ሁቱዎች በዋናው መንገድ ወደ ኪቩ ሐይቅ ሲተሙ አየሁ - ከመካከላቸው በመቶዎች የሚቆጠሩት የኢንተርሃምዌን የደንብ ልብስ ለብሰው ገጀራ ይዘዋል፡፡
‹‹ወይ አምላኬ›› አልኩ ተሸከርካሪው ላይ እንደገና ወድቄ፡፡ ‹‹ድጋሚ አያምጣው!›› ሁቱዎቹ መንገድ እንዲለቁና እንዲያሳልፉን የተሸከርካሪውን ጡሩንባ እየነፋን በተጨናነቀው መንገድ እናዘግም ገባን፡፡ ኢንተርሃምዌዎቹ ካስቆሙን ወይም ተሸከርካሪያችን ከተበላሸ በደቂቃዎች ውስጥ ይረባረቡብናል፡፡ መታጠቢያ ቤቱን ለቅቄ ከወጣሁ ወዲህ ይህን ያህል ፈርቼ አላውቅም፡፡
‹‹እባክህ አምላኬ›› ስል ጸለይኩ፡፡ ‹‹ይህን ያህል አምጥተኸናል - አሁን ቀሪውንም ጎዳና ውሰደን! እነዚህን ገዳዮችም አሳውርልን … እዚህ ተሸከርካሪ ጀርባ ላይ እንዲያዩ አታድርጋቸው፡፡ መሐሪው ጌታ ሆይ! ከነዚህ ጥላቻ ከተሞላባቸው ዓይኖቻቸው ሰውረን!››
ወደ ሩአግ ምሽግ ከሚወስደን መንገዳችን ከግማሽ በላይ እንደሄድን ተሸከርካሪው ቆመ፡፡ ፈረንሳዊው መኰንን ወደ ኋላ መጥቶ ሸራውን ገለጠና ‹‹በአካባቢው ተኩስ አለ የሚል ወሬ ደርሶናል፤ ስለሆነም በማናቸውም ሁኔታ ቢሆን ተኩስን የማስቆም ግዴታ አለብን፡፡ ስለዚህ ልንመለስ ስለሆነ የግድ እዚህ መውረድ አለባችሁ፡፡›› አሳስቼ የሰማሁት መሰለኝ፡፡ ‹‹መልሰህ ትወስደናለህ ማለት ነው፣ አይደል?››
‹‹አይ፣ መጠለያውን ልንዘጋው ስለሆነ ብትመለሱም የምታርፉበት ስፍራ የለም፡፡ እዚህ መውረድ አለባችሁ… አሁኑኑ፡፡ ይቅርታ እንግዲህ ኢማኪዩሌ፡፡›› ባለፉት ጥቂት ሳምንታት መኰንኑን በደንብ አውቄዋለሁ፡፡ ሁቱ ገዳዮችን ስለሚጠላ ቱትሲዎችን በተቻለው መጠን ለመርዳት እንደሚፈልግ ተናግሯል፤ ስለሆነም በታጠቁ ኢንተርሃምዌዎች እጅ ሊጥለን ነው ብዬ ላምን አልቻልኩም፡፡ እርሱን ለማሳመን ከተሽከርካሪው ወረድኩ፡፡ ‹‹እባክህ፣ መኰንን ሆይ፣ እዚህ ከተውከን ምን እንደሚከሰትብን ከማንም በላይ ታውቃለህ፡፡ በዙሪያችን ገዳዮቹ እያንዣበቡ ነው! እባክህ ተለመነኝ … የሩአግ ምሽግ ከዚህ በኋላ ግፋ ቢል አንድ ኪሎሜትር ስለሚርቅ እባክህ እዚያ አድርሰን፤ አሊያም መልሰህ ውሰደን … እዚህ ለእርድ አትተወን!››
‹‹ይቅርታ ኢማኪዩሌ፡፡ ትዕዛዝ አለብኝ፡፡››
‹‹እባክህ መኰንን ብትወስደን ምናለ!››
‹‹አይ! ሰዎችሽን አውርጅልኝ፡፡ መሄድ አለብን፡፡››
አንድ ደርዘን ገደማ ኢንተርሃምዌዎች አሥር ጫማ በሚሆን ርቀት እየተከታተሉን፣ የምንነጋገረውን እየሰሙና ፍላጎታቸው በጣም አይሎ ስለቆሙ እየተከሰተ ያለውን ነገር ልናምን አልቻልንም፡፡ ጨነቀኝ፤ መሬቷም ዞረችብኝ፣ ለአንድ አፍታ እንኳን የማየው ነገር የቁጡ ፊቶችን ብዥታ ሆነ፡፡ ራሴን በተሸከርካሪው አንድ ጎን ላይ አረጋግቼ ቆሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በመሬት ላይ ያሉትን አስከሬኖች ምንነት አወቅሁ - መንገዱን ተከትሎ ዓይኔ እስከሚያየው ድረስ ሳማትር አስከሬኖች በየቦታው ወድቀዋል፡፡
መኰንኑን ቀና ብዬ አይቼ በዓይኖቼ ለመጨረሻ ጊዜ ተለማመጥኩት፡፡ ረብ-አልባ ነው - ወይ ፍንክች አለ፡፡ ምናልባት ቄሱና ሌሎቹ ስለ ፈረንሳውያኑ የተናገሩት ልክ ነው ማለት ነው፡፡ እውነት እዚህ የመጡት ገዳዮቹን ለመርዳት ይሆን? ይኸው በእርግጠኝነት ለሞት ሊተዉን ነው፡፡
ለጓደኞቼ ‹‹ኑ ውረዱ›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ሁላችሁም ውረዱ … ፈረንጆቹ እዚህ ትተውን ሊሄዱ ነው፡፡››
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ስድስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የጌታዬ_ሥራ
፡
ሰዎች በመንገድ ላይ ለመዘዋወር እንኳን በሚፈሩበት ከተማ ሥራ የት እንደማገኝ የሚያውቀው አምላክ ነው፡፡ ውድቅዳቂ ፈንጂዎች የኪጋሊን መንገዶች ሞልተዋቸዋል፤ ለመሥራት ከፈለግሁ ግን በነዚህ ጎዳናዎች ሥራን እያነፈነፍኩ መኳተን ይኖርብኛል፡፡ የሕዝብ ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎች መንቀሳቀሳቸውን ትተዋል፤ ለአነስተኞቹም ማጓጓዣዎች የምከፍለው ምንም ገንዘብ አልነበረኝም፡፡
ፋሪን በቤቱ አቅራቢያ ያሉ ክፍት የሥራ ቦታ ያላቸውን ድርጅቶችን ያውቅ እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹አሁን ማንም እየቀጠረ ስላልሆነ አማራጮችሽ በጣም ውሱን ናቸው›› ሲል መለሰልኝ፡፡ ‹‹ያለው ብቸኛ አማራጭ የተመድ ነው … እዚያ ለመግባት ግን እንግሊዝኛ መናገር ያስፈልጋል፡፡››
በአእምሮዬ የሆነ ነገር ብልጭ አለልኝ፡፡ በእርግጥ! እግዚአብሔር በመታጠቢያ ክፍሉ እንግሊዝኛ እንዳጠና ያደረገኝ ዋነኛው ምክንያት እኮ የተመድ ነው፡፡ በተመድ የመሥራት ሕልምም ነበረኝ፡፡
በዚያን ምሽት ልብሶቼን በሚገባ አጥቤ አምላክ በተመድ ሥራ እንዳገኝ ያግዘኝ ዘንድ ጸለይኩ፡፡ በመጨረሻ እንግሊዝኛዬን በሥራ ላይ የማውልበት መሆኑን አስቤ በጣም ተደስቼ አብዛኛውን የሌሊቱን ጊዜ መስታወት ሳይና ራሴን በራሴ ያስተማርኳቸውን ሐረጋት ስለማመድ ቆየሁ፡፡
‹‹እንደምን አደራችሁ››
‹‹እንዴት ነዎት?››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡›› ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡››
‹‹ሩዋንዳዊት ነኝ፡፡››
‹‹ቡታሬ ባለው ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ አጥንቻለሁ፡፡››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡››
አቤት! እንዴት ደስ ይላል! ትክክለኛ የእንግሊዝኛ አረፍተ ነገሮችን መናገር ጀምሬያለሁ፤ ነገ በአዲስ ቋንቋ እነጋገራለሁ … ከዚያም አዲሱን ሥራዬን እሠራለሁ! ተመስገን አምላኬ!
ልክ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ላይ በተመድ ሕንጻ በር ፊት ለፊት ሄጄ ቆሜያለሁ፡፡ ጋናዊ ዘበኛ እንግሊዝኛ በሚመስል ቋንቋ ሞቅ አድርጎ ሰላምታ ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንደምን አደርሽ፣ ምን ልርዳሽ?›› ያለኝ ይመስለኛል፡፡ እኔ የሰማሁት ግን ‹‹ታታታ ታታታ ታታታታ?›› ዓይነት ነገር ነው፡፡ ምንም እንዳለ አንዳች ፍንጭ ባላገኝም የገባኝ አስመሰልኩ፡፡ ራሴን ከፍ፣ አገጬን ወጣ አድርጌ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው›› አልኩ በእንግሊዝኛ፡፡
ውይ፡፡ የዓይኖቹ አኳኋን አነጋገሬ እንዴት አስቂኝ እንደሆነበት ነገረኝ፡፡ ቢሆንም ግን እንደገና ሞከርኩ፡፡ ይህን ሁሉ ርቀት የመጣሁት ተመለሽ ለመባል አልነበረም፡፡ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው››
‹‹አሃ! ሩዋንዳዊት ነሽ… የምትችይው ፈረንሳይኛ መሆን አለበት›› አለኝ፡፡ ፈገግ ብዬ በአዎንታ ራሴን ነቀነቅሁ፡፡ ዋናውን በር ከፍቶልኝ ሌላ ዘበኛ ወደ አንዲት ትንሽ የእንግዳ መቀበያ ክፍል ወሰደኝ፤ ብዙ ቅጻቅጾችን ሞልቼ እንድጠብቅ ተነገረኝ፡፡ ጠበቅሁም … ጠበቅሁ… ጠበቅሁ … ጠበቅሁ፡፡ የተመድ ሠራተኞች ማታ ከሥራ ሲወጡ እንግዳ ተቀባይዋን ሥራውን እስካገኝ ምን ያክል መጠበቅ እንዳለብኝ ጠየኳት፡፡
‹‹ረጅም ጊዜ ትጠብቂያለሽ ውዴ … ሥራ የለም፡፡››
ወደ ቤቴ ተበሳጭቼ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ ሄድኩ፡፡ በተመድ መሥራት ዕጣ ፈንታዬ - የማልመውና ቆርጬ የተነሣሁበት ጉዳይ ነው፡፡ ፈጣሪ እዚያ እንድሠራ ከፈቀደ ከግቤ ከመድረስ ምንም አያስቆመኝም፡፡
በቀጣዩም ቀን ተመለስኩ፣ እነዚያኑ ቅጾች ሞላሁና ከሰዓቱን ጠበቅሁ፡፡ በቀጣዩም ቀን ይህንኑ አደረግሁ፤ በቀጣዩም፤ በቀጣዩም፡፡ ቅጾችን ስሞላና ስጠብቅ ከሁለት ሳምንታት በላይ ፈጀሁ፡፡ በየቀኑ ወደ ቤቴ ስሄድ እንግዳ ተቀባይዋ ‹‹እኔ አንቺን ብሆን ተመልሼ አልመጣም ነበር ውዴ፡፡ ምንም ሥራ እኮ የለም›› ትለኛለች፡፡ በሁለተኛው ሳምንት መጨረሻ ተስፋዬ እየተሟጠጠ መጣ፡፡ ሥራ ሳላገኝ ወደ አሎይዜ ቤት መሄድ አስፈራኝ፡፡ ስለሆነም ለራሴ አዝኜ በቤታችን ሰፈር በፈራረሱ መንገዶች እዞር ገባሁ፡፡ በራሴ ዐቅም ላይ ለማተኮር ከአምላክ ጋር ጸጥታ የተሞላበት ተግባቦት እያደረግሁ ለመቀመጥ ፈለግሁ፤ ለዚያ ተመስጦ ግን የአሎይዜ ቤት በጣም ረብሻ የሚበዛበት ነው፡፡ እርስዎ አመኑኝም አላመኙኝ ከአምላኬ ጋር ለሰዓታት ያለማቋረጥ የማወራበትን በቄሱ መታጠቢያ ክፍል ያሳለፍኩትን ወቅት ናፈቅሁ፡፡ በነዚያ ረጃጅም ጸጥ ያሉ ጸሎቶቼ ወቅት ልቤን የሞላበትን ደስታና ሰላም አስታወስኩ
- ከዚያ በኋላ አገኝ የነበረውን የአእምሮ ንጽሕናም ጭምር፡፡
ከአሎይዜ ቤት ሁለት ግቢ አልፎ ወደተቃጠለ ቤት ፍርሥራሽ ሄድኩ፡፡ በጉልበቶቼ በተቃጠለው ፍርሥራሽና በተሰባበረው መስታወት ላይ ተንበርክኬ ጸሎቶቼን ጀመርኩ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ጴጥሮስ ሌሊቱን ሙሉ ዐሳ ለማጥመድ ቢሞክርም ምንም ሳይዝ ቀርቶ ተስፋው ቢሟጠጥ፤ አንተ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሄዶ እንዲያጠምድ ነገርከው - እናም ብዙ ዐሳ አጠመደ! በጣም ደስተኛም ሆነ! እኔንም ታዲያ ወደ ተመድ ስለመራኸኝ እስካሁን ይህን ሁሉ ቀን ሥራ ‹እንዳጠመድኩ› አለሁ፡፡ ግን ምንም ዓሶች እዚህ የሉም፡፡ እግዚአብሔር፣ ምን እንደማደርግ አላውቅም፡፡ ገንዘብ የለኝም፤ ልብሶቼ እየተበጣጠሱ ነው፤ ሥራም አያስገኙኝም፡፡ ስለዚህ እገዛህን እፈልጋለሁ፡፡ እነዚህን የተመድ ሰዎች እንዲያዩኝና ጥሩ የጽሕፈት ቤት ሥራ እንዲሰጡኝ አድርግ፤ አንተ እንደምፈልገው ታውቃለህ፡፡ አግዘኝ፤ እኔም በበኩሌ ራሴን አግዛለሁ! ይሁን ይደረግልኝ፡፡››
ራሴን አጸዳድቼና የፈራረሰውን ቤት ትቼ በታደሰ የራስ መተማመን ሄድኩ፡፡ እግዚአብሔርን እገዛውን ጠየቅሁት፤ የምፈልገው አሁን እንዲከሰት ማድረጉ የራሴ ድርሻ እንደሆነ ታውቆኛል፡፡ በተመድ መሥራት የምፈልገውን በአእምሮዬ መቅረጽ ጀመርኩ - ማስታወሻ መያዝ፣ ስልክ መመለስና ጠቃሚ ውሳኔዎች ሲደረጉ ማገዝ፡፡ ወደ ቤት ስሄድ የተመዱን ሥራዬን አንዴ ካገኘሁ በኋላ ስለሚያስፈልጉኝ ነገሮች ሳስብ ቆየሁ፡፡ የተወሰኑ ለሰው ፊት የሚቀርቡ ልብሶች ሊኖሩኝ ይገባል፤ እናም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀኩበት ምስክር ወረቀትና ዩኒቨርሲቲ ለሦስት ዓመታት መከታተሌን የሚያረጋግጥ መረጃ ያስፈልጉኛል፡፡ ያለመታደል ሆኖ ሁሉም ንብረቶቼ አራት ሰዓት በተሽከርካሪ በሚያስነዳው ቡታሬ በሚገኘው በትምህርት ቤት የመኝታ ክፍሌ ናቸው፤ እንደሚታወቀው ወደዚያ ለመሄድ ደግሞ የምከፍለው ገንዘብ የለኝም፡፡
በሐሳብ በጣም ተውጬ አንድ ተሸከርካሪ በአጠገቤ አልፎ ነጂው ስሜን ሲጣራ ልብ አላልኩትም ማለት እችላለሁ - በዩኒቨርሲቲዬ መምህር የሆነው ዶክተር አቤል፡፡ ‹‹መች አወቅሁሽ ኢማኪዩሌ›› አለኝ፡፡ በጣም ከስተሻል! በመትረፍሽ በጣም ተደስቻለሁ … እንዲያው ምግብስ እየበላሽ ነው? የምትኖሪበትስ ቦታ አለሽ?›› ዶክተር አቤል የህክምና ዶክተር በመሆኑ ስላለፍኩበት ሁኔታና ስለጤናዬ ጉዳይ ጠየቀኝ፡፡ ለማገገም እንዲያግዘኝ ከእርሱ፣ ከሚስቱና ከቤተሰቡ ጋር ቡታሬ እንድኖር ቢጋብዘኝም አመስግኜው የምቆይባቸው ቤተሰብ እንዳሉኝ ነገርኩት፡፡ በቅርቡ ግን ቡታሬ የሚሄድ ከሆነ እንዲወስደኝ ነገርኩት፡፡
‹‹ምን ችግር አለ? በእርግጥ ነገ ሂያጅ ነኝ፡፡››
እንደገና የዕድል ገጠመኝ ነው ብዬ ባሰብኩት በዚህ ጉዳይ የአምላክን
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ስድስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የጌታዬ_ሥራ
፡
ሰዎች በመንገድ ላይ ለመዘዋወር እንኳን በሚፈሩበት ከተማ ሥራ የት እንደማገኝ የሚያውቀው አምላክ ነው፡፡ ውድቅዳቂ ፈንጂዎች የኪጋሊን መንገዶች ሞልተዋቸዋል፤ ለመሥራት ከፈለግሁ ግን በነዚህ ጎዳናዎች ሥራን እያነፈነፍኩ መኳተን ይኖርብኛል፡፡ የሕዝብ ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎች መንቀሳቀሳቸውን ትተዋል፤ ለአነስተኞቹም ማጓጓዣዎች የምከፍለው ምንም ገንዘብ አልነበረኝም፡፡
ፋሪን በቤቱ አቅራቢያ ያሉ ክፍት የሥራ ቦታ ያላቸውን ድርጅቶችን ያውቅ እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹አሁን ማንም እየቀጠረ ስላልሆነ አማራጮችሽ በጣም ውሱን ናቸው›› ሲል መለሰልኝ፡፡ ‹‹ያለው ብቸኛ አማራጭ የተመድ ነው … እዚያ ለመግባት ግን እንግሊዝኛ መናገር ያስፈልጋል፡፡››
በአእምሮዬ የሆነ ነገር ብልጭ አለልኝ፡፡ በእርግጥ! እግዚአብሔር በመታጠቢያ ክፍሉ እንግሊዝኛ እንዳጠና ያደረገኝ ዋነኛው ምክንያት እኮ የተመድ ነው፡፡ በተመድ የመሥራት ሕልምም ነበረኝ፡፡
በዚያን ምሽት ልብሶቼን በሚገባ አጥቤ አምላክ በተመድ ሥራ እንዳገኝ ያግዘኝ ዘንድ ጸለይኩ፡፡ በመጨረሻ እንግሊዝኛዬን በሥራ ላይ የማውልበት መሆኑን አስቤ በጣም ተደስቼ አብዛኛውን የሌሊቱን ጊዜ መስታወት ሳይና ራሴን በራሴ ያስተማርኳቸውን ሐረጋት ስለማመድ ቆየሁ፡፡
‹‹እንደምን አደራችሁ››
‹‹እንዴት ነዎት?››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡›› ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡››
‹‹ሩዋንዳዊት ነኝ፡፡››
‹‹ቡታሬ ባለው ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ አጥንቻለሁ፡፡››
‹‹ሥራ ፈልጌ ነው፡፡››
አቤት! እንዴት ደስ ይላል! ትክክለኛ የእንግሊዝኛ አረፍተ ነገሮችን መናገር ጀምሬያለሁ፤ ነገ በአዲስ ቋንቋ እነጋገራለሁ … ከዚያም አዲሱን ሥራዬን እሠራለሁ! ተመስገን አምላኬ!
ልክ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ላይ በተመድ ሕንጻ በር ፊት ለፊት ሄጄ ቆሜያለሁ፡፡ ጋናዊ ዘበኛ እንግሊዝኛ በሚመስል ቋንቋ ሞቅ አድርጎ ሰላምታ ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንደምን አደርሽ፣ ምን ልርዳሽ?›› ያለኝ ይመስለኛል፡፡ እኔ የሰማሁት ግን ‹‹ታታታ ታታታ ታታታታ?›› ዓይነት ነገር ነው፡፡ ምንም እንዳለ አንዳች ፍንጭ ባላገኝም የገባኝ አስመሰልኩ፡፡ ራሴን ከፍ፣ አገጬን ወጣ አድርጌ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው›› አልኩ በእንግሊዝኛ፡፡
ውይ፡፡ የዓይኖቹ አኳኋን አነጋገሬ እንዴት አስቂኝ እንደሆነበት ነገረኝ፡፡ ቢሆንም ግን እንደገና ሞከርኩ፡፡ ይህን ሁሉ ርቀት የመጣሁት ተመለሽ ለመባል አልነበረም፡፡ ‹‹እንዴት ነዎት? ስሜ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ ነው፡፡ ሥራ ፈልጌ ነው››
‹‹አሃ! ሩዋንዳዊት ነሽ… የምትችይው ፈረንሳይኛ መሆን አለበት›› አለኝ፡፡ ፈገግ ብዬ በአዎንታ ራሴን ነቀነቅሁ፡፡ ዋናውን በር ከፍቶልኝ ሌላ ዘበኛ ወደ አንዲት ትንሽ የእንግዳ መቀበያ ክፍል ወሰደኝ፤ ብዙ ቅጻቅጾችን ሞልቼ እንድጠብቅ ተነገረኝ፡፡ ጠበቅሁም … ጠበቅሁ… ጠበቅሁ … ጠበቅሁ፡፡ የተመድ ሠራተኞች ማታ ከሥራ ሲወጡ እንግዳ ተቀባይዋን ሥራውን እስካገኝ ምን ያክል መጠበቅ እንዳለብኝ ጠየኳት፡፡
‹‹ረጅም ጊዜ ትጠብቂያለሽ ውዴ … ሥራ የለም፡፡››
ወደ ቤቴ ተበሳጭቼ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ ሄድኩ፡፡ በተመድ መሥራት ዕጣ ፈንታዬ - የማልመውና ቆርጬ የተነሣሁበት ጉዳይ ነው፡፡ ፈጣሪ እዚያ እንድሠራ ከፈቀደ ከግቤ ከመድረስ ምንም አያስቆመኝም፡፡
በቀጣዩም ቀን ተመለስኩ፣ እነዚያኑ ቅጾች ሞላሁና ከሰዓቱን ጠበቅሁ፡፡ በቀጣዩም ቀን ይህንኑ አደረግሁ፤ በቀጣዩም፤ በቀጣዩም፡፡ ቅጾችን ስሞላና ስጠብቅ ከሁለት ሳምንታት በላይ ፈጀሁ፡፡ በየቀኑ ወደ ቤቴ ስሄድ እንግዳ ተቀባይዋ ‹‹እኔ አንቺን ብሆን ተመልሼ አልመጣም ነበር ውዴ፡፡ ምንም ሥራ እኮ የለም›› ትለኛለች፡፡ በሁለተኛው ሳምንት መጨረሻ ተስፋዬ እየተሟጠጠ መጣ፡፡ ሥራ ሳላገኝ ወደ አሎይዜ ቤት መሄድ አስፈራኝ፡፡ ስለሆነም ለራሴ አዝኜ በቤታችን ሰፈር በፈራረሱ መንገዶች እዞር ገባሁ፡፡ በራሴ ዐቅም ላይ ለማተኮር ከአምላክ ጋር ጸጥታ የተሞላበት ተግባቦት እያደረግሁ ለመቀመጥ ፈለግሁ፤ ለዚያ ተመስጦ ግን የአሎይዜ ቤት በጣም ረብሻ የሚበዛበት ነው፡፡ እርስዎ አመኑኝም አላመኙኝ ከአምላኬ ጋር ለሰዓታት ያለማቋረጥ የማወራበትን በቄሱ መታጠቢያ ክፍል ያሳለፍኩትን ወቅት ናፈቅሁ፡፡ በነዚያ ረጃጅም ጸጥ ያሉ ጸሎቶቼ ወቅት ልቤን የሞላበትን ደስታና ሰላም አስታወስኩ
- ከዚያ በኋላ አገኝ የነበረውን የአእምሮ ንጽሕናም ጭምር፡፡
ከአሎይዜ ቤት ሁለት ግቢ አልፎ ወደተቃጠለ ቤት ፍርሥራሽ ሄድኩ፡፡ በጉልበቶቼ በተቃጠለው ፍርሥራሽና በተሰባበረው መስታወት ላይ ተንበርክኬ ጸሎቶቼን ጀመርኩ፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ጴጥሮስ ሌሊቱን ሙሉ ዐሳ ለማጥመድ ቢሞክርም ምንም ሳይዝ ቀርቶ ተስፋው ቢሟጠጥ፤ አንተ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሄዶ እንዲያጠምድ ነገርከው - እናም ብዙ ዐሳ አጠመደ! በጣም ደስተኛም ሆነ! እኔንም ታዲያ ወደ ተመድ ስለመራኸኝ እስካሁን ይህን ሁሉ ቀን ሥራ ‹እንዳጠመድኩ› አለሁ፡፡ ግን ምንም ዓሶች እዚህ የሉም፡፡ እግዚአብሔር፣ ምን እንደማደርግ አላውቅም፡፡ ገንዘብ የለኝም፤ ልብሶቼ እየተበጣጠሱ ነው፤ ሥራም አያስገኙኝም፡፡ ስለዚህ እገዛህን እፈልጋለሁ፡፡ እነዚህን የተመድ ሰዎች እንዲያዩኝና ጥሩ የጽሕፈት ቤት ሥራ እንዲሰጡኝ አድርግ፤ አንተ እንደምፈልገው ታውቃለህ፡፡ አግዘኝ፤ እኔም በበኩሌ ራሴን አግዛለሁ! ይሁን ይደረግልኝ፡፡››
ራሴን አጸዳድቼና የፈራረሰውን ቤት ትቼ በታደሰ የራስ መተማመን ሄድኩ፡፡ እግዚአብሔርን እገዛውን ጠየቅሁት፤ የምፈልገው አሁን እንዲከሰት ማድረጉ የራሴ ድርሻ እንደሆነ ታውቆኛል፡፡ በተመድ መሥራት የምፈልገውን በአእምሮዬ መቅረጽ ጀመርኩ - ማስታወሻ መያዝ፣ ስልክ መመለስና ጠቃሚ ውሳኔዎች ሲደረጉ ማገዝ፡፡ ወደ ቤት ስሄድ የተመዱን ሥራዬን አንዴ ካገኘሁ በኋላ ስለሚያስፈልጉኝ ነገሮች ሳስብ ቆየሁ፡፡ የተወሰኑ ለሰው ፊት የሚቀርቡ ልብሶች ሊኖሩኝ ይገባል፤ እናም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀኩበት ምስክር ወረቀትና ዩኒቨርሲቲ ለሦስት ዓመታት መከታተሌን የሚያረጋግጥ መረጃ ያስፈልጉኛል፡፡ ያለመታደል ሆኖ ሁሉም ንብረቶቼ አራት ሰዓት በተሽከርካሪ በሚያስነዳው ቡታሬ በሚገኘው በትምህርት ቤት የመኝታ ክፍሌ ናቸው፤ እንደሚታወቀው ወደዚያ ለመሄድ ደግሞ የምከፍለው ገንዘብ የለኝም፡፡
በሐሳብ በጣም ተውጬ አንድ ተሸከርካሪ በአጠገቤ አልፎ ነጂው ስሜን ሲጣራ ልብ አላልኩትም ማለት እችላለሁ - በዩኒቨርሲቲዬ መምህር የሆነው ዶክተር አቤል፡፡ ‹‹መች አወቅሁሽ ኢማኪዩሌ›› አለኝ፡፡ በጣም ከስተሻል! በመትረፍሽ በጣም ተደስቻለሁ … እንዲያው ምግብስ እየበላሽ ነው? የምትኖሪበትስ ቦታ አለሽ?›› ዶክተር አቤል የህክምና ዶክተር በመሆኑ ስላለፍኩበት ሁኔታና ስለጤናዬ ጉዳይ ጠየቀኝ፡፡ ለማገገም እንዲያግዘኝ ከእርሱ፣ ከሚስቱና ከቤተሰቡ ጋር ቡታሬ እንድኖር ቢጋብዘኝም አመስግኜው የምቆይባቸው ቤተሰብ እንዳሉኝ ነገርኩት፡፡ በቅርቡ ግን ቡታሬ የሚሄድ ከሆነ እንዲወስደኝ ነገርኩት፡፡
‹‹ምን ችግር አለ? በእርግጥ ነገ ሂያጅ ነኝ፡፡››
እንደገና የዕድል ገጠመኝ ነው ብዬ ባሰብኩት በዚህ ጉዳይ የአምላክን
👍4
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሰባት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ሙታኑን_ስቀብር
፡
፡
‹‹ወላጆችሽ የት ነው የሚኖሩት?›› ይህ ጥያቄ በተመድ ሥራዬን ከጀመርኩ ከጥቂት ወራት በኋላ የቀረበልኝ፡፡
‹‹ልቤ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር በሕይወት የሉም›› በማለት በትዕግሥት መለስኩ፡፡
‹‹በዘር ፍጅቱ ተገድለዋል፡፡››
የተመድ ሰቆቃዬን ለመርሳት የምችልበት ስፍራ አይደለም፡፡ እዚያ የሚሰሩት አብዛኞቹ ከሀገሪቱ ውጪ የመጡ ስለሆኑ የቤተሰቤን ዕጣ ፈንታ ሲያውቁ የዘውጌ አባላት አብዛኞቹ በተገደሉበት ሁኔታ እኔ እንዴት ልተርፍ አንደቻልኩ ለማወቅ በጣም ይጓጓሉ፡፡
‹‹ይቅርታ›› አሉኝ እያዋሩኝ ያሉት ሰውዬ፡፡ ‹‹አላወቅሁም፡፡ እንዳላበሳጨሁሽ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡›› ስማቸው ኮሎኔል ጉዬ ሲሆን ወደ ሩዋንዳ አገሪቱን በማረጋጋቱ ተግባር ለማገዝ የመጣው የተመድ ሰላም አስከባሪ ጦር አዛዥ ሴኔጋላዊ ናቸው፡፡ እኔን ስለማበሳጨት እንዳይጨነቁ ለኮሎኔሉ ነገርኳቸው፡፡ ጥያቄ መጠየቅ ያለፍኩትን ሁሉ ከግምት ውስጥ ሳስገባው ከሚያሳስቡኝ ነገሮች በጣም ዝቅተኛውን ደረጃ ነው የሚይዘው፡፡ አሁንም ቢሆን ከጦርነቱ ወዲህ ባላያቸውም አክስቶችና በመጣሁበት ኪቡዬ ክፍለሀገር የሚኖር አጎት እንዳለኝ አሳወቅኋቸው፡፡
‹‹አሃ፣ ኪቡዬ … እዚያ የሰፈሩ የተወሰኑ ወታደሮች አሉኝ›› በማለት መለሱልኝ፡፡ ‹‹ዘመዶችሽን መጠየቅ ካስፈለገሽ ላጓጉዝሽና ራሴ ላጅብሽ እችላለሁ፡፡ ጓደኛም ከፈልግሽ ማምጣት ትችያለሽ፡፡››
በሀገሪቱ መዘዋወር ያን ጊዜም ቢሆን አስቸጋሪና አደጋ ላይ የሚጥል ስለሆነ የእርሳቸው ግብዣ ትልቅ ችሮታ ነው፡፡
‹‹በእውነት? መቼ እንደሆነ ይንገሩኝና እንሄዳለን ኮሎኔል፡፡›› ከሁለት ሳምንታት በኋላ ሳራና እኔ ወታደራዊ ጠያራ ላይ በቀበቶ ታስረን አንዳችን የሌላችንን እጆች እየያዝንና በደስታ እየሣቅን በሩዋንዳ አረንጓዴ ተራሮች ላይ እንበር ጀመር፡፡ ሁለታችንም በአየር በርረን ስለማናውቅ ኮሎኔሉ የመብረር እድሉን ሲሰጡን እውነት አልመሰለንም ነበር!
ውቧን አገሬን ቁልቁል ሳያት የዘር ጭፍጨፋውን አስቀያሚ እውነታ ማመን አስቸገረኝ፡፡ በነዚያ ጨለማ ቀናት ምን ያህል ጊዜ ነው ወፍ ሆኜ በተወለድኩ ብዬ የተመኘሁት? ምን ያህልስ ጊዜ ነው ከመታጠቢያ ቤት እስር ቤቴ ወጥቼ ከአሰቃቂው ሰቆቃ በላይ ርቄ መብረርን ያለምኩት? እና አሁን እዚህ ወንጀሉ የተፈጸመበትን ስፍራ ተመልሼ ለመጎብኘት ይኸው እበር ይዣለሁ፡፡ ከማታባ አምልጬ ኪጋሊ ለመድረስ ስንት ጊዜ ፈጅቶብኝ እንደነበር አውርቼልዎታለሁ - ለመመለስ ይኸው 30 ደቂቃ ብቻ ፈጀብኝና አረፈው፡፡
ኤይማብል ከኔ ጋር ቢሆን ብዬ ተመኘሁ፤ ግን አልተቻለም፡፡ የመልዕክት መላላኪያ አገልግሎቱ ገና ቀርፋፋ ሲሆን፤ በዚያም ላይ ከእርሱ የመልስ ደብዳቤ እንኳን ለማግኘት ሳምንታት ፈጅቶብኛል፡፡ ከኔ ይህ ደብዳቤ ስለደረሰውና በሕይወት መኖሬን በማወቁ በጣም ደስተኛ ስለሆነ ስሜቱን ለመግለጽ ቃላት ሊያገኝልኝ እንዳልቻለ ገልጾ ጻፈልኝ፡፡ በዘር ፍጅቱ ወቅት የዜና ዘገባዎችን ይከታተል ስለነበር ሁሉም የቤተሰባችን አባል ከሌላው ሩዋንዳ ውስጥ ካለ ሁሉም ቱትሲ ጋር ወድሟል ብሎ አምኖ ተስፋ ቆርጦ ነበር፡፡ ለመገደል ካልሆነ በቀር በዘር ፍጅቱ ወቅት ወደ ሀገሪቱ የሚመለስበት ምንም መንገድ አልነበረውም፡፡
ለመምጣት ችግር የሆነበት ደግሞ በወቅቱ ለመመለስ ወጪውን መሸፈን አለመቻሉ ነው፡፡ ተማሪ ስለሆነ ገቢ የለውም፣ የሚኖረው 5 000 ኪሎሜትር ርቆ በሴኔጋል ነው፡፡ የአየር መሳፈሪያ ወጭው ብቻ 2 000 የአሜሪካን ዶላር ይፈጃል፤ ይህም የማይታሰብ ነው! ሙሉ ወጭውን ሸፍኖ የሚያስተምረው የአውሮፓ ድርጅትም ሩዋንዳ በጣም አደገኛ የጦርነት ቀጠና ስለሆነ ወደዚያ የምትሄድበትን ክፍያ አልከፍልልህም ይለዋል፡፡ ወንድሜ ትምህርቱን አቋርጦ መጥቶ ከኔ ጋር ለመኖር ቢፈልግም እማማንና አባባን የሚያኮራበት ሁነኛ መንገድ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት መጨረስ እንደሆነ ነገርኩት፡፡ በየሳምንቱ ለመጻጻፍ፣ ለወደፊቱ ለመጠያየቅና ገንዘብም ለማጠራቀም ተስማማን፡፡ እናም አሁን ወደ ማታባ ላገኘሁት የነጻ የአየር ጉዞ ምስጋና ይግባውና ቤታችንን ያለ ብቸኛው ቀሪ ወንድሜ እጎበኛለሁ፡፡
ትንሿ ወታደራዊ ጠያራ መሬት ላይ ካረፈች በኋላ ኮሎኔል ጉዬ ትራኦሬ ለሚባል ብርቱ ወጣት መኰንን አደራ ብለው በወታደሮቹ ምሽግ አስቀምጠውን ይሄዳሉ፡፡ እርሱም ለእያንዳንዱ ወታደር የኮሎኔል ጉዬ ልጆች ናቸው ብሎ አስተዋወቀን፡፡ ከዚህን ጊዜ በፊት በነበሩኝ የወታደር ምሽግ ቆይታዎቼ አግኝቼው የማላውቀውን አገኘሁ - ሳራና እኔ የየራሳችን ክፍል፣ የምንተኛባቸው አልጋዎች፣ ምርጥ ምግብ ብሎም የእያንዳንዱ ወታደር አክብሮትና እገዛ ተቸረን፡፡ እንዲያውም እስከ ንጋት ድረስ ባህላዊ የሴኔጋል ዘፈኖችን ሲዘፍኑና እርስ በርሳቸው ሲቀላለዱ አብረን አነጋን፡፡ ሳራ በአቀባበሉ ደስ ከመሰኘቷም በላይ ደኅንነት ሲሰማት እኔም አገሬ በመግባቴ ደስ ተሰኘሁ፡፡
በማግስቱ ወደ መንደሬ ለመሄድ ስምንት ኪሎሜትር የሚርቀውን የእግር መንገድ ለመጓዝ ስዘገጃጅ መኰንን ትራኦሬ ስለደህንነታችን ያለውን ሥጋት ይናገር ጀመር፡፡ የዘር ፍጅቱ ቢያበቃም በሀገሪቱ ግልጽ የሆነ ጥላቻ ስለነገሰ በዚያን ወቅትም ግድያ ይፈጸማል፡፡ መኰንኑ በትጥቅ አጀብ ሊልከን ወሰነ - አጀቡም ከሁለት ደርዘን ያላነሱ ወታደሮችንና አምስት ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችን ያጠቃልላል፡፡ ማታባ በጀግና ኩራት እንገባለን እንጂ እንደ ተመላሽ ስደተኛ አንሹለከለክም፡፡ በዚያች መንደር ያን ያህል ጊዜ በፍራቻና ሥጋት ተሸሽጌባታለሁ፤ አሁን ግን ራሴን ቀና አድርጌ መሄዴ መልካም ነው፡፡
በልጅነቴ በጣም በማውቀው ሰማይ ስር ተሸከርካሪዎቻችንን ስንነዳ ስሜቴ በፍጥነት ወደ ኃይለኛ ብስጭት ተለወጠ፡፡ ወንድሞቼና እኔ ብዙውን ጊዜ እንሄድበት ወደነበረው መንገድ ስንገባ ማልቀስ ጀመርኩ፤ ከዚያም በወቅቱ ጭር ባለው እናቴ ታስተምርበት በነበረው ትምህርት ቤት አልፈን አባታችንን ተከትለን በጠዋት ኪቩ ሐይቅ ወርደን ልንዋኝ በምናልፍበት መንገድ ቁልቁል ወረድን፡፡ ሳራ እጇን በትከሻዬ አድርጋ ልታጽናናኝ ብትሞክርም አልሆነም - መጽናናት የምችል አልነበርኩም፡፡ በፈራረሱ መስኮቶችና በተዘጉ የውጪ በሮች አጮልቀው የሚያዩን ፊቶች ጥላ ይታየኛል … ብዙ ወገኖቼን አሳደው የገደሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ፊቶች፡፡ ብዙዎቹን የቱትሲዎችን ቤቶች ራሳቸው ካቃጠሉ በኋላ አሁን ብቻቸውን ቆመው ያሉትን ብቸኛ ቤቶች በንብረትነት ይዘዋቸዋል፡፡ ከዚያም የራሴ ቤት ጋ ደረስን፡፡
ጣራ የለ፣ መስኮት የለ፣ በር የለ፤ ሙሉ በሙሉ ወድሟል፡፡ ገዳዮቹ ለጭፍጨፋቸው ሲዘገጃጁ እኛ ለቀናት ሬድዮ ስናዳምጥበት የነበረውን የተቃጠለውን መሬት የተወሰኑ ከፊል ግንቦች እየጠበቁት ዘብ ቆመዋል፡፡ አንድ ወቅት የወላጆቼ ሕልም የነበሩትን ባዶ ክፍሎች እየቃኘሁ በድንጋይ መዋቅሩ ውስጥ ተዟዟርኩ፡፡ የተጎዱ የቤት እቃዎችም ሆኑ የተቃጠሉ ልብሶች አሻራ የለም - ማንም ሊገምት እንደሚችለው ቤቱ ከመጋየቱ በፊት ንብረታችን ተዘርፏል፡፡
ብዙ በሕይወት የተረፉ ቱትሲ ጎረቤቶቻችን ወታደራዊ አጀባችንን አይተው ሰላም ሊሉኝ መጡ፡፡ በተደበቅኩባቸው ጊዜያት ስለተከሰቱት መጥፎ ነገሮች ነገሩኝ፤ እናቴ በተቀበረችበት ቦታ ላይ ሆነንም እምዬ እናቴ አንዴት እንደተገደለች ያስረዱኝ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሰባት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ሙታኑን_ስቀብር
፡
፡
‹‹ወላጆችሽ የት ነው የሚኖሩት?›› ይህ ጥያቄ በተመድ ሥራዬን ከጀመርኩ ከጥቂት ወራት በኋላ የቀረበልኝ፡፡
‹‹ልቤ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር በሕይወት የሉም›› በማለት በትዕግሥት መለስኩ፡፡
‹‹በዘር ፍጅቱ ተገድለዋል፡፡››
የተመድ ሰቆቃዬን ለመርሳት የምችልበት ስፍራ አይደለም፡፡ እዚያ የሚሰሩት አብዛኞቹ ከሀገሪቱ ውጪ የመጡ ስለሆኑ የቤተሰቤን ዕጣ ፈንታ ሲያውቁ የዘውጌ አባላት አብዛኞቹ በተገደሉበት ሁኔታ እኔ እንዴት ልተርፍ አንደቻልኩ ለማወቅ በጣም ይጓጓሉ፡፡
‹‹ይቅርታ›› አሉኝ እያዋሩኝ ያሉት ሰውዬ፡፡ ‹‹አላወቅሁም፡፡ እንዳላበሳጨሁሽ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡›› ስማቸው ኮሎኔል ጉዬ ሲሆን ወደ ሩዋንዳ አገሪቱን በማረጋጋቱ ተግባር ለማገዝ የመጣው የተመድ ሰላም አስከባሪ ጦር አዛዥ ሴኔጋላዊ ናቸው፡፡ እኔን ስለማበሳጨት እንዳይጨነቁ ለኮሎኔሉ ነገርኳቸው፡፡ ጥያቄ መጠየቅ ያለፍኩትን ሁሉ ከግምት ውስጥ ሳስገባው ከሚያሳስቡኝ ነገሮች በጣም ዝቅተኛውን ደረጃ ነው የሚይዘው፡፡ አሁንም ቢሆን ከጦርነቱ ወዲህ ባላያቸውም አክስቶችና በመጣሁበት ኪቡዬ ክፍለሀገር የሚኖር አጎት እንዳለኝ አሳወቅኋቸው፡፡
‹‹አሃ፣ ኪቡዬ … እዚያ የሰፈሩ የተወሰኑ ወታደሮች አሉኝ›› በማለት መለሱልኝ፡፡ ‹‹ዘመዶችሽን መጠየቅ ካስፈለገሽ ላጓጉዝሽና ራሴ ላጅብሽ እችላለሁ፡፡ ጓደኛም ከፈልግሽ ማምጣት ትችያለሽ፡፡››
በሀገሪቱ መዘዋወር ያን ጊዜም ቢሆን አስቸጋሪና አደጋ ላይ የሚጥል ስለሆነ የእርሳቸው ግብዣ ትልቅ ችሮታ ነው፡፡
‹‹በእውነት? መቼ እንደሆነ ይንገሩኝና እንሄዳለን ኮሎኔል፡፡›› ከሁለት ሳምንታት በኋላ ሳራና እኔ ወታደራዊ ጠያራ ላይ በቀበቶ ታስረን አንዳችን የሌላችንን እጆች እየያዝንና በደስታ እየሣቅን በሩዋንዳ አረንጓዴ ተራሮች ላይ እንበር ጀመር፡፡ ሁለታችንም በአየር በርረን ስለማናውቅ ኮሎኔሉ የመብረር እድሉን ሲሰጡን እውነት አልመሰለንም ነበር!
ውቧን አገሬን ቁልቁል ሳያት የዘር ጭፍጨፋውን አስቀያሚ እውነታ ማመን አስቸገረኝ፡፡ በነዚያ ጨለማ ቀናት ምን ያህል ጊዜ ነው ወፍ ሆኜ በተወለድኩ ብዬ የተመኘሁት? ምን ያህልስ ጊዜ ነው ከመታጠቢያ ቤት እስር ቤቴ ወጥቼ ከአሰቃቂው ሰቆቃ በላይ ርቄ መብረርን ያለምኩት? እና አሁን እዚህ ወንጀሉ የተፈጸመበትን ስፍራ ተመልሼ ለመጎብኘት ይኸው እበር ይዣለሁ፡፡ ከማታባ አምልጬ ኪጋሊ ለመድረስ ስንት ጊዜ ፈጅቶብኝ እንደነበር አውርቼልዎታለሁ - ለመመለስ ይኸው 30 ደቂቃ ብቻ ፈጀብኝና አረፈው፡፡
ኤይማብል ከኔ ጋር ቢሆን ብዬ ተመኘሁ፤ ግን አልተቻለም፡፡ የመልዕክት መላላኪያ አገልግሎቱ ገና ቀርፋፋ ሲሆን፤ በዚያም ላይ ከእርሱ የመልስ ደብዳቤ እንኳን ለማግኘት ሳምንታት ፈጅቶብኛል፡፡ ከኔ ይህ ደብዳቤ ስለደረሰውና በሕይወት መኖሬን በማወቁ በጣም ደስተኛ ስለሆነ ስሜቱን ለመግለጽ ቃላት ሊያገኝልኝ እንዳልቻለ ገልጾ ጻፈልኝ፡፡ በዘር ፍጅቱ ወቅት የዜና ዘገባዎችን ይከታተል ስለነበር ሁሉም የቤተሰባችን አባል ከሌላው ሩዋንዳ ውስጥ ካለ ሁሉም ቱትሲ ጋር ወድሟል ብሎ አምኖ ተስፋ ቆርጦ ነበር፡፡ ለመገደል ካልሆነ በቀር በዘር ፍጅቱ ወቅት ወደ ሀገሪቱ የሚመለስበት ምንም መንገድ አልነበረውም፡፡
ለመምጣት ችግር የሆነበት ደግሞ በወቅቱ ለመመለስ ወጪውን መሸፈን አለመቻሉ ነው፡፡ ተማሪ ስለሆነ ገቢ የለውም፣ የሚኖረው 5 000 ኪሎሜትር ርቆ በሴኔጋል ነው፡፡ የአየር መሳፈሪያ ወጭው ብቻ 2 000 የአሜሪካን ዶላር ይፈጃል፤ ይህም የማይታሰብ ነው! ሙሉ ወጭውን ሸፍኖ የሚያስተምረው የአውሮፓ ድርጅትም ሩዋንዳ በጣም አደገኛ የጦርነት ቀጠና ስለሆነ ወደዚያ የምትሄድበትን ክፍያ አልከፍልልህም ይለዋል፡፡ ወንድሜ ትምህርቱን አቋርጦ መጥቶ ከኔ ጋር ለመኖር ቢፈልግም እማማንና አባባን የሚያኮራበት ሁነኛ መንገድ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት መጨረስ እንደሆነ ነገርኩት፡፡ በየሳምንቱ ለመጻጻፍ፣ ለወደፊቱ ለመጠያየቅና ገንዘብም ለማጠራቀም ተስማማን፡፡ እናም አሁን ወደ ማታባ ላገኘሁት የነጻ የአየር ጉዞ ምስጋና ይግባውና ቤታችንን ያለ ብቸኛው ቀሪ ወንድሜ እጎበኛለሁ፡፡
ትንሿ ወታደራዊ ጠያራ መሬት ላይ ካረፈች በኋላ ኮሎኔል ጉዬ ትራኦሬ ለሚባል ብርቱ ወጣት መኰንን አደራ ብለው በወታደሮቹ ምሽግ አስቀምጠውን ይሄዳሉ፡፡ እርሱም ለእያንዳንዱ ወታደር የኮሎኔል ጉዬ ልጆች ናቸው ብሎ አስተዋወቀን፡፡ ከዚህን ጊዜ በፊት በነበሩኝ የወታደር ምሽግ ቆይታዎቼ አግኝቼው የማላውቀውን አገኘሁ - ሳራና እኔ የየራሳችን ክፍል፣ የምንተኛባቸው አልጋዎች፣ ምርጥ ምግብ ብሎም የእያንዳንዱ ወታደር አክብሮትና እገዛ ተቸረን፡፡ እንዲያውም እስከ ንጋት ድረስ ባህላዊ የሴኔጋል ዘፈኖችን ሲዘፍኑና እርስ በርሳቸው ሲቀላለዱ አብረን አነጋን፡፡ ሳራ በአቀባበሉ ደስ ከመሰኘቷም በላይ ደኅንነት ሲሰማት እኔም አገሬ በመግባቴ ደስ ተሰኘሁ፡፡
በማግስቱ ወደ መንደሬ ለመሄድ ስምንት ኪሎሜትር የሚርቀውን የእግር መንገድ ለመጓዝ ስዘገጃጅ መኰንን ትራኦሬ ስለደህንነታችን ያለውን ሥጋት ይናገር ጀመር፡፡ የዘር ፍጅቱ ቢያበቃም በሀገሪቱ ግልጽ የሆነ ጥላቻ ስለነገሰ በዚያን ወቅትም ግድያ ይፈጸማል፡፡ መኰንኑ በትጥቅ አጀብ ሊልከን ወሰነ - አጀቡም ከሁለት ደርዘን ያላነሱ ወታደሮችንና አምስት ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችን ያጠቃልላል፡፡ ማታባ በጀግና ኩራት እንገባለን እንጂ እንደ ተመላሽ ስደተኛ አንሹለከለክም፡፡ በዚያች መንደር ያን ያህል ጊዜ በፍራቻና ሥጋት ተሸሽጌባታለሁ፤ አሁን ግን ራሴን ቀና አድርጌ መሄዴ መልካም ነው፡፡
በልጅነቴ በጣም በማውቀው ሰማይ ስር ተሸከርካሪዎቻችንን ስንነዳ ስሜቴ በፍጥነት ወደ ኃይለኛ ብስጭት ተለወጠ፡፡ ወንድሞቼና እኔ ብዙውን ጊዜ እንሄድበት ወደነበረው መንገድ ስንገባ ማልቀስ ጀመርኩ፤ ከዚያም በወቅቱ ጭር ባለው እናቴ ታስተምርበት በነበረው ትምህርት ቤት አልፈን አባታችንን ተከትለን በጠዋት ኪቩ ሐይቅ ወርደን ልንዋኝ በምናልፍበት መንገድ ቁልቁል ወረድን፡፡ ሳራ እጇን በትከሻዬ አድርጋ ልታጽናናኝ ብትሞክርም አልሆነም - መጽናናት የምችል አልነበርኩም፡፡ በፈራረሱ መስኮቶችና በተዘጉ የውጪ በሮች አጮልቀው የሚያዩን ፊቶች ጥላ ይታየኛል … ብዙ ወገኖቼን አሳደው የገደሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ፊቶች፡፡ ብዙዎቹን የቱትሲዎችን ቤቶች ራሳቸው ካቃጠሉ በኋላ አሁን ብቻቸውን ቆመው ያሉትን ብቸኛ ቤቶች በንብረትነት ይዘዋቸዋል፡፡ ከዚያም የራሴ ቤት ጋ ደረስን፡፡
ጣራ የለ፣ መስኮት የለ፣ በር የለ፤ ሙሉ በሙሉ ወድሟል፡፡ ገዳዮቹ ለጭፍጨፋቸው ሲዘገጃጁ እኛ ለቀናት ሬድዮ ስናዳምጥበት የነበረውን የተቃጠለውን መሬት የተወሰኑ ከፊል ግንቦች እየጠበቁት ዘብ ቆመዋል፡፡ አንድ ወቅት የወላጆቼ ሕልም የነበሩትን ባዶ ክፍሎች እየቃኘሁ በድንጋይ መዋቅሩ ውስጥ ተዟዟርኩ፡፡ የተጎዱ የቤት እቃዎችም ሆኑ የተቃጠሉ ልብሶች አሻራ የለም - ማንም ሊገምት እንደሚችለው ቤቱ ከመጋየቱ በፊት ንብረታችን ተዘርፏል፡፡
ብዙ በሕይወት የተረፉ ቱትሲ ጎረቤቶቻችን ወታደራዊ አጀባችንን አይተው ሰላም ሊሉኝ መጡ፡፡ በተደበቅኩባቸው ጊዜያት ስለተከሰቱት መጥፎ ነገሮች ነገሩኝ፤ እናቴ በተቀበረችበት ቦታ ላይ ሆነንም እምዬ እናቴ አንዴት እንደተገደለች ያስረዱኝ
👍1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ድህረ_ታሪክ
፡
፡
#አዲስ_ፍቅር_አዲስ_ሕይወት
አንድ የተሰበረ ልብ ለማገገም ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል ብሎ ለመተንበይ ያዳግታል፤ እኔ ግን ተባርኬያለሁ፡- በእግዚአብሔር እርዳታ ልቤ ከሁለት ዓመት በኋላ ሌላ ለማፍቀር ችሏል፡፡ ስድን ግን የኖርኩት ዝምተኛና አመዛዛኝ ሕይወት ነው ፡፡በተመድ እየሠራሁና ከሳራ ቤተሰብ ጋር እየኖርኩ በትርፍ ጊዜዬ ኪጋሊ በሚገኝ አንድ የእጓለማውታ ማሳደጊያ በደርዘኖች ለሚቆጠሩ የተሸበሩ ብቸኛ ልጆች በታላቅ እህትነት በማገልገል በበጎ ፈቃደኝነት ሥራ አሳለፍኩ፡፡ በፈረንሳይ ምሽግ እንከባከባቸው የነበሩትን ሁለት ወንድማማቾች ሥራዬ ብዬ ብፈልጋቸውም ላገኛቸው አልቻልኩም፡፡ ይሁን እንጂ ሌሎች ብዙ ፍቅር ፈላጊ ወጣቶችን አግኝቻለሁ፡፡ በ1995 መጨረሻ ከኤይማብል ጋር ተገናኘሁ፡፡ ነጻ የትምህርት ዕድል የሰጠው አካል በሩዋንዳ ሰላም ተመልሷል ብሎ ስላመነ ወደ አገሩ የሚመጣበትን የአየር መጓጓዣ ወጪ ሸፈነለት፡፡ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ጊዜ ተጻጽፈናል፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያትም በስልክ አውርተናል፡፡ በአካል ለመገናኘት ግን በመንፈስ አልተዘጋጀንም፡፡ በአየር ማረፊያው የተገናኘንበትን ሁኔታ መቼም አልረሳውም፡፡ ልቦቻችንን ከክፉ እየጠበቅን ይመስል ስሜታችን ፈንቅሎ በመውጣት ወይም እንባ በመራጨት ፈንታ አቀባበሉ በስሱ ተከናወነ፡፡ ተቃቀፍን፣ ተሳሳምን፤ እኔ የእርሱን፣ እርሱም የኔን ህመም ላለመንካት ግን ተፈራርተን ጥንቃቄ አደረግን፡፡ ዓይን ለዓይን ለመተያየት ተፈራራን፡፡ እውነተኛ ስሜታችን ከወጣ መቆጣጠር እንደሚያቅተን አውቀን ከበደን፡፡ ማልቀስ ከጀመርን ማቆሚያ እንደሌለን ገብቶናል፡፡
ወንድሜና እኔ ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ምግብ ቤት ሄደን ራት እየበላን ስለ እርሱ ትምህርትና ስለኔ ሥራ እያወራንና በጓደኞቼም ቀልዶች እየሣቅን እናስመስል ያዝን፡፡ በዚያ ሌሊት ግን ብቻዬን መኝታዬ ላይ ሆኜ እንባዬን ዘረገፍኩት፡፡ ወንድሜም እንዲሁ እንዳደረገ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን አብሮ መሆኑ ይበልጥ ቀለለን፡፡ ምንም እንኳን እርስ በርስ መተያየቱ የቤተሰባችንን አሳዛኝ ፍጻሜ አሰቃቂ ትውስታ የሚቀሰቅስብን ቢሆንም በጣም ስለምንዋደድ አንዳችን በሌላችን መኖር ምቾት ተሰምቶናል፡፡ ህመሙን ለመቋቋም የሚያግዘኝን ጥንካሬ እንዳገኘሁ ልነግረውና ላጽናናውም ፈልጌያለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የማያጽናኑት ዓይነት እንዳልሆነ ወዲያውኑ ታወቀኝ፡፡ ከአፍታ በኋላም በቤተሰባችን ስለተከሰተው ሰቆቃ ላለማንሳት ሳንነጋገር እንደተስማማን ገባን፡፡ የቤተሰባችንን አባላት ሁሉ በስም ጠቃቀስን፡፡ ያኔም ቢሆን አሁንም በሕይወት እንዳሉ አድርገን ነበር ያወራነው - የምንቋቋምበት ብቸኛው መንገዳችን ይህ ነው፡፡ ለቀጣዮቹም ሁለት ዓመታት በደብዳቤና በስልክ እንደዚያው ስናደርግ ቆየን፡፡ ኤይማብል የእንስሳት ሕክምና የድህረ ምረቃ መርሃ-ግብሩን ጨርሶ ወደ ኪጋሊ ሲመለስም ሁኔታው አልተቀየረም፡፡ በየቀኑ በአካል ብንገናኝም ስለ ዘር ጭፍጨፋው የምናወራው አንድ የሆነ ሰው ላይ የተከሰተ ይመስል እንዲያው በደምሳሳው ነው፡፡ የእማማንና የዳማሲንን መቃብርም ሲያይ እንኳን እንዳካሂደው አልጠየቀኝም፤ ብቻውን ሄደ፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያው እንዲሁ አለን፡፡ ኤይማብል አሁንም የሚኖረው ኪጋሊ ነው፤ ስኬታማ ሐኪም ሲሆን ቆንጅዬ ሚስትና ልጆች አሉት፡፡ እርስ በርሳችን በጣም እንዋደዳለን፤ ከመቼውም በላይ ቅርርብ አለን፡፡ በየጊዜው እንደዋወላለን፤ ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜም እንጻጻፋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላም ስለቤተሰባችን ስንነጋገር ‹ነበር› አንልም፡፡ ትዝታቸውን ህያው አድርጎ ማቆያ መንገዳችን ይህ ነው ብዬ እገምታለሁ፡፡
ብዙ ምሽቶቼን በአቅራቢያዬ ባለና ሁለተኛ ቤቴ ሆኖ በነበረው በጀስዊቶች ማእከል በጸሎትና ተመስጦ ተጠምጄ አሳልፋሁ፡፡ በተደበቅሁባቸው ረጅም ወራት ወቅት ያዳነኝን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረኝን የጠበቀ ቁርኝቴን በድጋሚ የጀመርኩት በነዚያ ርጭ ባሉ ስፍራዎች ነው፡፡
ልቤ ቀስ በቀስ ሲያገግምልኝ የወደፊቱን ሕይወቴን አብሬ የሚጋራ አንድ ልዩ የራሴ የምለው ሰውና የምንከባከበው ቤተሰብ ማለም ጀመርኩ፡፡ ግን ሐሳብ ገባኝ … ከዮሃንስ ጋር የነበረኝን ሁኔታ አስታወስኩና በቀላሉ ሊሰበር የሚችለውን ልቤን የትም ለማይደርስና በሚያሳምም መልኩ ለሚቋጭ ግንኙነት ላለመስጠት ወሰንኩ፡፡ ስለዚህ ችግር ወይም ፈተና በሚያጋጥመኝ ጊዜ ሁሉ እንደማደርገው የአምላክን እገዛ ጠየቅሁ፡፡ በገነት የሚሆን ጋብቻ ከፈለግሁ ከአምላኬ በተሻለ የሚኩለኝና የሚድረኝ ከቶ ማን ይኖራል?
መጽሐፍ ቅዱስ ከጠየቅን እንደምናገኝ ይነግረናል፤ በእርግጥም ያንን አደረግሁ፡፡ እግዚአብሔርን የማልመውን ሰው እንዲያመጣልኝ ጠየቅሁት፡፡ ራሴን ማጭበርበር አልፈልግሁም - እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የምፈልገው ሰው ምን ዓይነት እንደሆነ በጣም ግልጽ ማድረግ ነበረብኝ፡፡ ስለሆነም ወረቀት ይዤ ተቀመጥኩና ላገባው የምፈልገውን ሰው ፊት ነደፍኩ፡፡ ከዚያም ቁመቱንና ሌሎቹን ገጽታዎቹን ዘረዘርኩ፡፡ ጠንካራ ማንነትና ምቹ ስብዕና ያለው፣ ደግ፣ አፍቃሪና ርህሩህ፣ ተጨዋች፣ ምግባረመልካም፣ ማንነቴን የሚወድልኝ፣ እንደኔ ልጆችን የሚያፈቅርና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን የሚወድ ሰው ይሰጠኝ ዘንድ ጠየቅሁ፡፡
ለእግዚአብሔር ቀን አልቆረጥኩለትም፡፡ በዘር፣ በዜግነት ወይንም የቆዳ ቀለም ላይም ምንም ገደብ አልጣልኩ፡፡ በዓለም ላይ ከአምስት ቢሊየን በላይ ሰዎች እንደመኖራቸው - ጌታዬ የሕይወቴን አጋር የሚልክበትና እኔም የምጠብቅበት አግባብ ያለው የቆይታ ጊዜ ስድስት ወራት እንዲሆን አቀድኩ፡፡ አንድ ማስጠንቀቂያንም ጨመርኩ፡- ድንግል ማርያምን እጅግ ስለምወዳት እግዚአብሔር ከእምነቴ ተመሳሳይ የሆነ ባል ቢልክልኝ እንደሚሻል ነገርኩት፡፡ በሃይማኖት ሳቢያ በትዳሬ ምንም ዓይነት ውጥረት እንደማይኖር ማረጋገጥ እንዲሁም ባሌ እግዚአብሔርን እኔ በማመልከው መልኩ እንዲያመልክ ፈለግሁ፡፡
ምን እንደምፈልግ በትክክል ካወቅሁ በኋላ ፍላጎቴን አልመው ጀመር፡፡ ጌታ የተመኘሁትን ባርኮ እንደሚሰጠኝ፣ የልቤ መሻት እንደሚሆንልኝና የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነ አምኜ ሁሉንም ለእርሱ ተውኩት፡፡ ሂደቱን ለማፋጠን የአባቴን ቀይና ነጭ መቁጠሪያ አወጣሁና ባሌ እንዲመጣልኝ መጸለይ ጀመርኩ፡፡ ከሦስት ወራት በኋላም መጣልኝ፡- ከእግዚአብሔር የተላከውና የተመድ የሸለመኝ አቶ ብርያን ብላክ ከአሜሪካ ድረስ ከተፍ አለ! የነገሩ መገጣጠም ደሞ ብርያን ወደ ሀገሪቱ የመጣው የዘር ማጥፋቱን በማቀድ የተሳተፉትን ለፍርድ ለማቅረብ የሚጥረውን የተመዱን ዓለም አቀፍ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት በማቋቋሙ ሂደት ለማገዝ ሆኖ እርፍ፡፡ ብርያን ለተመድ ለብዙ ዓመታት ስለሠራ ገዳዮቹን ፍትሃዊ ቅጣት እንዲያገኙ የሚያደርገው የተልዕኮው አካል በመሆኑ ይደሰታል፡፡ በግሌ እርሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ ነው፡፡
ብርያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ ግቢ ሳየው በትክክል እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የጠየቅሁትን ሰውዬ መሰለኝ፡፡ በኋላ በአዳራሹ ሳልፈውና በዓይኖቹ የነበረውን ጥልቅ እርጋታ ሳይ እርሱ እንደሆነ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ግን በእግዚአብሔር እምነቴን ስላደረግሁ ብርያንን ወደኔ እንዲያመጣው ጠበቅሁት አመጣልኛ ብርያን አብረን እንድንዝናና ጋብዞኝ ግሩም ጊዜ አሳለፍን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ድህረ_ታሪክ
፡
፡
#አዲስ_ፍቅር_አዲስ_ሕይወት
አንድ የተሰበረ ልብ ለማገገም ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል ብሎ ለመተንበይ ያዳግታል፤ እኔ ግን ተባርኬያለሁ፡- በእግዚአብሔር እርዳታ ልቤ ከሁለት ዓመት በኋላ ሌላ ለማፍቀር ችሏል፡፡ ስድን ግን የኖርኩት ዝምተኛና አመዛዛኝ ሕይወት ነው ፡፡በተመድ እየሠራሁና ከሳራ ቤተሰብ ጋር እየኖርኩ በትርፍ ጊዜዬ ኪጋሊ በሚገኝ አንድ የእጓለማውታ ማሳደጊያ በደርዘኖች ለሚቆጠሩ የተሸበሩ ብቸኛ ልጆች በታላቅ እህትነት በማገልገል በበጎ ፈቃደኝነት ሥራ አሳለፍኩ፡፡ በፈረንሳይ ምሽግ እንከባከባቸው የነበሩትን ሁለት ወንድማማቾች ሥራዬ ብዬ ብፈልጋቸውም ላገኛቸው አልቻልኩም፡፡ ይሁን እንጂ ሌሎች ብዙ ፍቅር ፈላጊ ወጣቶችን አግኝቻለሁ፡፡ በ1995 መጨረሻ ከኤይማብል ጋር ተገናኘሁ፡፡ ነጻ የትምህርት ዕድል የሰጠው አካል በሩዋንዳ ሰላም ተመልሷል ብሎ ስላመነ ወደ አገሩ የሚመጣበትን የአየር መጓጓዣ ወጪ ሸፈነለት፡፡ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ጊዜ ተጻጽፈናል፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያትም በስልክ አውርተናል፡፡ በአካል ለመገናኘት ግን በመንፈስ አልተዘጋጀንም፡፡ በአየር ማረፊያው የተገናኘንበትን ሁኔታ መቼም አልረሳውም፡፡ ልቦቻችንን ከክፉ እየጠበቅን ይመስል ስሜታችን ፈንቅሎ በመውጣት ወይም እንባ በመራጨት ፈንታ አቀባበሉ በስሱ ተከናወነ፡፡ ተቃቀፍን፣ ተሳሳምን፤ እኔ የእርሱን፣ እርሱም የኔን ህመም ላለመንካት ግን ተፈራርተን ጥንቃቄ አደረግን፡፡ ዓይን ለዓይን ለመተያየት ተፈራራን፡፡ እውነተኛ ስሜታችን ከወጣ መቆጣጠር እንደሚያቅተን አውቀን ከበደን፡፡ ማልቀስ ከጀመርን ማቆሚያ እንደሌለን ገብቶናል፡፡
ወንድሜና እኔ ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ምግብ ቤት ሄደን ራት እየበላን ስለ እርሱ ትምህርትና ስለኔ ሥራ እያወራንና በጓደኞቼም ቀልዶች እየሣቅን እናስመስል ያዝን፡፡ በዚያ ሌሊት ግን ብቻዬን መኝታዬ ላይ ሆኜ እንባዬን ዘረገፍኩት፡፡ ወንድሜም እንዲሁ እንዳደረገ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን አብሮ መሆኑ ይበልጥ ቀለለን፡፡ ምንም እንኳን እርስ በርስ መተያየቱ የቤተሰባችንን አሳዛኝ ፍጻሜ አሰቃቂ ትውስታ የሚቀሰቅስብን ቢሆንም በጣም ስለምንዋደድ አንዳችን በሌላችን መኖር ምቾት ተሰምቶናል፡፡ ህመሙን ለመቋቋም የሚያግዘኝን ጥንካሬ እንዳገኘሁ ልነግረውና ላጽናናውም ፈልጌያለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የማያጽናኑት ዓይነት እንዳልሆነ ወዲያውኑ ታወቀኝ፡፡ ከአፍታ በኋላም በቤተሰባችን ስለተከሰተው ሰቆቃ ላለማንሳት ሳንነጋገር እንደተስማማን ገባን፡፡ የቤተሰባችንን አባላት ሁሉ በስም ጠቃቀስን፡፡ ያኔም ቢሆን አሁንም በሕይወት እንዳሉ አድርገን ነበር ያወራነው - የምንቋቋምበት ብቸኛው መንገዳችን ይህ ነው፡፡ ለቀጣዮቹም ሁለት ዓመታት በደብዳቤና በስልክ እንደዚያው ስናደርግ ቆየን፡፡ ኤይማብል የእንስሳት ሕክምና የድህረ ምረቃ መርሃ-ግብሩን ጨርሶ ወደ ኪጋሊ ሲመለስም ሁኔታው አልተቀየረም፡፡ በየቀኑ በአካል ብንገናኝም ስለ ዘር ጭፍጨፋው የምናወራው አንድ የሆነ ሰው ላይ የተከሰተ ይመስል እንዲያው በደምሳሳው ነው፡፡ የእማማንና የዳማሲንን መቃብርም ሲያይ እንኳን እንዳካሂደው አልጠየቀኝም፤ ብቻውን ሄደ፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያው እንዲሁ አለን፡፡ ኤይማብል አሁንም የሚኖረው ኪጋሊ ነው፤ ስኬታማ ሐኪም ሲሆን ቆንጅዬ ሚስትና ልጆች አሉት፡፡ እርስ በርሳችን በጣም እንዋደዳለን፤ ከመቼውም በላይ ቅርርብ አለን፡፡ በየጊዜው እንደዋወላለን፤ ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜም እንጻጻፋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላም ስለቤተሰባችን ስንነጋገር ‹ነበር› አንልም፡፡ ትዝታቸውን ህያው አድርጎ ማቆያ መንገዳችን ይህ ነው ብዬ እገምታለሁ፡፡
ብዙ ምሽቶቼን በአቅራቢያዬ ባለና ሁለተኛ ቤቴ ሆኖ በነበረው በጀስዊቶች ማእከል በጸሎትና ተመስጦ ተጠምጄ አሳልፋሁ፡፡ በተደበቅሁባቸው ረጅም ወራት ወቅት ያዳነኝን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረኝን የጠበቀ ቁርኝቴን በድጋሚ የጀመርኩት በነዚያ ርጭ ባሉ ስፍራዎች ነው፡፡
ልቤ ቀስ በቀስ ሲያገግምልኝ የወደፊቱን ሕይወቴን አብሬ የሚጋራ አንድ ልዩ የራሴ የምለው ሰውና የምንከባከበው ቤተሰብ ማለም ጀመርኩ፡፡ ግን ሐሳብ ገባኝ … ከዮሃንስ ጋር የነበረኝን ሁኔታ አስታወስኩና በቀላሉ ሊሰበር የሚችለውን ልቤን የትም ለማይደርስና በሚያሳምም መልኩ ለሚቋጭ ግንኙነት ላለመስጠት ወሰንኩ፡፡ ስለዚህ ችግር ወይም ፈተና በሚያጋጥመኝ ጊዜ ሁሉ እንደማደርገው የአምላክን እገዛ ጠየቅሁ፡፡ በገነት የሚሆን ጋብቻ ከፈለግሁ ከአምላኬ በተሻለ የሚኩለኝና የሚድረኝ ከቶ ማን ይኖራል?
መጽሐፍ ቅዱስ ከጠየቅን እንደምናገኝ ይነግረናል፤ በእርግጥም ያንን አደረግሁ፡፡ እግዚአብሔርን የማልመውን ሰው እንዲያመጣልኝ ጠየቅሁት፡፡ ራሴን ማጭበርበር አልፈልግሁም - እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የምፈልገው ሰው ምን ዓይነት እንደሆነ በጣም ግልጽ ማድረግ ነበረብኝ፡፡ ስለሆነም ወረቀት ይዤ ተቀመጥኩና ላገባው የምፈልገውን ሰው ፊት ነደፍኩ፡፡ ከዚያም ቁመቱንና ሌሎቹን ገጽታዎቹን ዘረዘርኩ፡፡ ጠንካራ ማንነትና ምቹ ስብዕና ያለው፣ ደግ፣ አፍቃሪና ርህሩህ፣ ተጨዋች፣ ምግባረመልካም፣ ማንነቴን የሚወድልኝ፣ እንደኔ ልጆችን የሚያፈቅርና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን የሚወድ ሰው ይሰጠኝ ዘንድ ጠየቅሁ፡፡
ለእግዚአብሔር ቀን አልቆረጥኩለትም፡፡ በዘር፣ በዜግነት ወይንም የቆዳ ቀለም ላይም ምንም ገደብ አልጣልኩ፡፡ በዓለም ላይ ከአምስት ቢሊየን በላይ ሰዎች እንደመኖራቸው - ጌታዬ የሕይወቴን አጋር የሚልክበትና እኔም የምጠብቅበት አግባብ ያለው የቆይታ ጊዜ ስድስት ወራት እንዲሆን አቀድኩ፡፡ አንድ ማስጠንቀቂያንም ጨመርኩ፡- ድንግል ማርያምን እጅግ ስለምወዳት እግዚአብሔር ከእምነቴ ተመሳሳይ የሆነ ባል ቢልክልኝ እንደሚሻል ነገርኩት፡፡ በሃይማኖት ሳቢያ በትዳሬ ምንም ዓይነት ውጥረት እንደማይኖር ማረጋገጥ እንዲሁም ባሌ እግዚአብሔርን እኔ በማመልከው መልኩ እንዲያመልክ ፈለግሁ፡፡
ምን እንደምፈልግ በትክክል ካወቅሁ በኋላ ፍላጎቴን አልመው ጀመር፡፡ ጌታ የተመኘሁትን ባርኮ እንደሚሰጠኝ፣ የልቤ መሻት እንደሚሆንልኝና የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነ አምኜ ሁሉንም ለእርሱ ተውኩት፡፡ ሂደቱን ለማፋጠን የአባቴን ቀይና ነጭ መቁጠሪያ አወጣሁና ባሌ እንዲመጣልኝ መጸለይ ጀመርኩ፡፡ ከሦስት ወራት በኋላም መጣልኝ፡- ከእግዚአብሔር የተላከውና የተመድ የሸለመኝ አቶ ብርያን ብላክ ከአሜሪካ ድረስ ከተፍ አለ! የነገሩ መገጣጠም ደሞ ብርያን ወደ ሀገሪቱ የመጣው የዘር ማጥፋቱን በማቀድ የተሳተፉትን ለፍርድ ለማቅረብ የሚጥረውን የተመዱን ዓለም አቀፍ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት በማቋቋሙ ሂደት ለማገዝ ሆኖ እርፍ፡፡ ብርያን ለተመድ ለብዙ ዓመታት ስለሠራ ገዳዮቹን ፍትሃዊ ቅጣት እንዲያገኙ የሚያደርገው የተልዕኮው አካል በመሆኑ ይደሰታል፡፡ በግሌ እርሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ ነው፡፡
ብርያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ ግቢ ሳየው በትክክል እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የጠየቅሁትን ሰውዬ መሰለኝ፡፡ በኋላ በአዳራሹ ሳልፈውና በዓይኖቹ የነበረውን ጥልቅ እርጋታ ሳይ እርሱ እንደሆነ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ግን በእግዚአብሔር እምነቴን ስላደረግሁ ብርያንን ወደኔ እንዲያመጣው ጠበቅሁት አመጣልኛ ብርያን አብረን እንድንዝናና ጋብዞኝ ግሩም ጊዜ አሳለፍን
👍2