አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
459 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሁቱትሲ


#ምዕራፍ_ሦስት


#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች

#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ

#ቅድመ_ከፍተኛ_ትምህርት

በሦስተኛውና በመጨረሻው ዓመት ጦርነት ከመፈንዳቱ በቀር ሕይወት በሊሴ ጥሩ ነበር፡፡
የ1990 የጥቅምት ወር የመጀመሪያዋ ቀን ከሰዓት ቆንጆና ብሩህ ነበረች፡፡ የክፍል ጓደኞቼና እኔ የግብረገብ ትምህርት ክፍለጊዜያችን እስኪጀምር እየጠበቅን መምህሩ ለምን እንደዘገየ እናስባለን፡፡ አቶ ጋሂጊ ለመግባባት የማያስቸግር፣ የተረጋጋና ምናልባትም ካገኘኋቸው ሰዎች ሁሉ ልስልስ ጸባይ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም በመጨረሻ እጆቹን አያይዞ ሲመጣና በክፍሉ ፊትለፊት ወደፊትና ወደኋላ ሄድ መለስ ሲል አንዳች ነገር እንደተከሰተ ገምተናል፡፡ አንደኛዋ ተማሪ ችግሩ ምን እንደሆነ ብትጠይቀውም ወደ እኛ ሳያይ መለስ ቀለስ ማለቱን ቀጠለ፡፡
መምህራችን አንዳች መጥፎ ዜና እንደደበቀንና ምን አልባትም የተንቀሳቃሽ ምስል ትዕይንት ምሽትን መነኩሲቶቹ ሰርዘውት እንደሆነ ሊነግረን ይሆናል ብዬ አሰብኩ፡፡ ጉዳዩ ግን ከዚያ የባሰ ነበር፡፡ በትምህርት ቤት ውስጥ የዜና ዘገባዎችን ማዳመጥ ስለማይፈቀድልን በመኖሪያ ቤቴ እንደነበረው ሁሉ ከዓለም ወሬ ተነጥያለሁ፡፡
‹‹በሀገሪቱ ላይ ጥቃት እንደተፈጸመ ሰማሁ›› ሲል አቶ ጋሂጊ በሃዘኔታ ነገረን፡፡ ‹‹በጣም አደገኛና በሁላችንም ላይ ለረጅም ጊዜ ተጽዕኖ የሚኖረው ይሆናል ብዬ እፈራለሁ፡፡››
ክፍሉ በጸጥታ ተዋጠ - ከዚያ ሁሉም ባንዴ ማውራት ጀመረ፣ ጥያቄ መጠያየቅ፣ ሩዋንዳን ማን ለምን እንደሚያጠቃት ለማወቅ መጠባበቅ፡፡
‹‹በዩጋንዳ የሚኖር የአማጽያን ቡድን የአገሪቱን ድንበር አቋርጧል›› ሲል መለሰልን፡፡ ‹‹በዋነኝነት ከሩዋንዳ የሄዱ ጥገኞች ልጆች ሲሆኑ ተሰባስበው ወደ ሀገሪቱ ለመግባት እየተዋጉ ነው፡፡ ከዚህ ስፍራ በስተሰሜን በኩል በአሁኑ ሰዓት በአማጽያንና በሩዋንዳ መንግሥት ወታደሮች መካከል ከባድ ውጊያ በመካሄድ ላይ ነው፡፡›› አቶ ጋሂጊ ፍርሃትና ንዴትን የሚያንጸባርቅ የጥያቄዎች ዝናብ ወረደበት፡፡ ‹‹ቱትሲዎቹ ሽፍቶች ግን ምንድን ነው የሚፈልጉት? ለምን ጦርነት ይከፍቱብናል? ትምህርት ቤቱ ጋር ከደረሱስ ምን ያደርጉን ይሆን?››
የሃፍረት ሙቀት በማጅራቴ ተሰማኝ፤ በማስደገፊያዬም ስር ለመደበቅ ፈለግሁ፡፡ በክፍሉ ውስጥ ካለነው 50 ተማሪዎች 47ቱ ሁቱዎች ናቸው፡፡ በጣም ስለፈራሁና ስለራሴ ስለተጨነቅሁ ሌሎቹን ሁለት ቱትሲ ልጃገረዶች ማየት እንኳን ተሳነኝ፡፡ በቱትሲነቴ ሳፍርና በሊሴም ተለይቼ ስታይ የመጀመሪያዬ ነው፡፡
‹‹አማጽያኑ ራሳቸውን የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር (ሩአግ) ብለው አደራጅተዋል፡፡ ቡድኑ ሩዋንዳን ከዓመታት በፊት ለቀው የሄዱና እንዳይመለሱ የተከለከሉ የቱትሲዎች ድርጅት ነው፡፡ እነዚህ የውጪ ዜጎች ወደ ሩዋንዳ በመግባት መንግሥታዊውን ለመያዝ ጦርነት አውጀውብናል›› አለ፡፡
ስለ ሩአግ ምንነት ግንዛቤው ነበረኝ፡፡ አባላቱ መንግሥትን ለመጣል ሲሉ ብቻ እንደማይዋጉም አውቃለሁ፡፡ እኩልነት በሰፈነባትና በነጻ ሀገር መኖርን ይፈልጋሉ፡፡ አብዛኞቹ የሩአግ ወታደሮች ስደተኞች ቱትሲዎች ወይንም ልጆቻቸው ናቸው፡፡
በ1959ና በ1973ቱ ችግሮች እንዲሁም ሁቱ ጽንፈኞች የግድያ ዘመቻዎችን ባካሄዱባቸው ሌሎች በርካታ ጊዜያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሕይወት ለማዳን ከሩዋንዳ ሸሽተዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ አማጽያኑን ‹‹የውጪ ዜጎች›› ያላቸው አብዛኞቹ እንደ ዩጋንዳና ዛየር ባሉ ጎረቤት ሀገራት ስላደጉ ነው - ያ የሆነው ግን ርዕሰ-ብሔር ሃብያሪማና ስደተኞች ፈጽሞ ወደ ሀገራቸው አንዳይመለሱ የሚከለክል ሕግ ስላወጡ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ግዙፍ የቱትሲ ስደተኞች ስብስብ እንዲፈጠር ያደረጉ ሲሆን አንድ ሙሉ የሩዋንዳ ቱትሲዎች ትውልድንም አንዴ እንኳን የእናት አገሩን አፈር ሳይረግጥ እንዲያድግ አስገድደዋል፡፡ አቶ ጋሂጊ ያንን ፈጽሞ ባይገልጽም ቱትሲዎች ራሳቸውን ከጽንፈኛ ሁቱዎች ለመከላከል በሞከሩ ቁጥር ግን ምን እንደሚከሰት ያውቃል፡፡ ለእኛ መጨነቁን ‹‹ይህ ለቱትሲዎች በጣም አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል - ይህን ዓይነት ነገር ወደ ብዙ ግድያዎች ሊያመራ ስለሚችል መንግሥትና አማጽያኑ ችግራቸውን እንዲፈቱና ደም መፋሰስ እንዲቆም እንጸልይ፡፡››
የዕለቱ ትምህርታችን በዚሁ አበቃ፡፡ ሴቶቹ ልጆች ግን የሚያወሩት ስለጥቃቱና ቱትሲ ወታደሮቹ ወደ ትምህርት ቤታችን ቢደርሱ ምን ማድረግ እንደሚኖርባቸው ብቻ ሆነ፡፡ ከሁለት ቱትሲ የክፍል ጓደኞቼ ጋር ጸጥ ብዬ ላለመታየት እየሞከርኩ ተቀመጥሁ፡፡ ቱትሲዎች እንዴት ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደተያዙ ሳስብ ሃፍረቴ ወደ ንዴት ተለወጠ፡፡ የመንግሥት ወታደሮችን አሸንፎ ለመድሎው ፍጻሜ ያበጅለት ዘንድ ተስፋ በማድረግ በልቤ ለሩአግ አጋርነቴን አሳየሁ፡፡ በመጨረሻ ግን ንዴቴ ወደ ፍራቻ የተቀየረው ስለመንደሬና ስለቤተሰቤ በተጨነቅሁ ጊዜ ነው፡፡ አምላኬ ቤተሰቤን ሰላም ያደርግልኝ ዘንድ ዓይኖቼን ጨፍኜ ተማጸንኩት - በወቅቱ ያለ-ነሱ እንዴት በሕይወት እንደምቆይ ስለማላውቅ፡፡
ብዙዎቹ ተማሪዎች ጦርነቱ አስከፊ በነበረበት በሰሜኑ ክፍል ዘመዶች ስለነበሯቸው የትምህርት ቤቱ ርዕሰ - መምህር የሬድዮ ዘገባ እንድናዳምጥና ስለ ክስተቱ እንድንረዳ ፈቀደልን፡፡ ብሄራዊው ሬድዮ የሚያስተላልፈው ዘገባ ከሞላ ጎደል የጥላቻ ውትወታ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዘጋቢዎቹ አማጽያኑ እንደ አውሬ በጫካ እንደሚኖሩ፣ የሰው ስጋ እንደሚበሉና ከዝንጀሮዎች ጋር ወሲብ እንደሚፈጽሙ አተቱ፡፡ የለየላቸው ሰይጣኖች ስለሆኑ ቀንድ አብቅለዋል ተባለ፡፡ ‹‹አማጽያን በረሮዎቹ›› በማናቸውም ስፍራና ጊዜ ሊተናኮሉ ስለሚችሉና መሰሪ ስለሆኑ ሩዋንዳውያን ራሳቸውን እንዲጠብቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው፡፡ እነዚህ ዘገባዎች ቀድሞውንም የተዛባ አመለካከት የነበራቸውን ልጃገረዶች አቀጣጠሏቸው፡፡ አንዷማ በጣም ፈርታ ስለነበር ልታስገድለኝ ነበር፡፡
ዳኒዳ ከመኝታ ቤት እህቶቼ አንዷ ስትሆን ስለአማጽያን ወታደሮቹ የተነገሩትን ሁሉንም አስፈሪ ገለጻዎች አምናቸዋለች፡፡ አንድ ምሽት ከመኝታ ቤቱ ውጪ ወደሚገኘው መታጠቢያ ክፍላችን ለመጠቀም ስሄድ ከእንቅልፏ ሳልቀሰቅሳት አልቀርም፡፡ ምሽቱ በጣም ይቀዘቅዝ ስለነበር እንዲሞቀኝ ትልቅ ፎጣዬን በራሴ አስሬ የሚረዝምብኝ የነበረ የሌሊት ልብስ ለብሻለሁ፡፡ ትንሽ ሳላስፈራ አልቀርም፣ ተመልሼ ለመግባት በሩን ለመክፈት ስሞክር ዳኒዳ ፊቴ ላይ በኃይል ዘጋችብኝ፡፡ ኡኡታዋን ስታቀልጠው ግቢው ተሸበረ፡፡
‹‹አድኑኝ! እርዱኝ! ወይኔ አምላኬ! ኧረ እርዱኝ፡፡ የሩአግ ወታደር ነው - ሊገድለን፣ ሊበላን መጣ፡፡ አቤት ቀንዶቹ!››
የዳኒዳን ጆሮ ሰንጥቆ የሚገባ ድምፅ ስላወቅሁት በእርጋታ ‹‹ዳኒዳ፣ እኔ እኮ ነኝ፣ ኢማኪዩሌ ነኝ፡፡ ወታደር አይደለሁም፡፡ ቀንድም የለኝ፤ ፎጣዬን ነው እኮ ራሴ ላይ ያሰርኩት!›› አልኳት፡፡
ሞቅ አድርገው የሚረግጡ እግሮች ከኮረኮንቹ ጎዳና በኩል ሰምቼ ዘወር ስል የትምህርት ቤታችን ትልቁ ዘበኛ በደረቴ ትይዩ ያነጣጠረ ጦር ይዞ በጨለማው ወደኔ ይገሰግሳል፡፡ ብርክ ይዞኝ ጉልበቴ ተሽመድምዶ መሬት ላይ ቁጭ አልኩ፡፡ ዘበኛው ከእኔ መጠነኛ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ! ኢማኪዩሌ፣ ገድዬሽ ነበር እኮ! ማናባቷ ነች እንደዚያ የምትጮኸው?›› አለ፡፡
በወቅቱ