ፋይል ውስጥ አንድ ደብዳቤ አውጥቶ ለዳኛው እንዲሰጥለት አደረገ፡፡ ዳኛውና አቃቤ ሕጉ የየራሳቸውን ፋይል እያወጡ ተመለከቱ፡፡የዚሁኑ ደብዳቤ ኮፒ ዶ/ር አድማሱም እንዲያነበው ተሰጠው፡፡ ዶክተሩ ከንፈሩ እየተርበተበተ በጸጥታ አንብቦ ከጨረሰ በኋላ፤
እና ይህ ደብዳቤ ከእኔ ጋር ምን ያገናኘዋል?'' በማለት ጮኸ ተናገረ:: ጠበቃዬ መልስ ሳይሰጥ በተረጋጋ መልኩ ሌላ ደብዳቤ እንዲሰጠው አደረገ፡፡ ዶ/ሩ ወረቀቱን እንደያዘ ጠበቃዬንና ዳኞቹን በየተራ አያቸው:: ፊቲ በላብ ተደፍቆ ደብዳቤውን ማንበብ ተያያዘው:: እንደጨረሰም : “ይህም ደብዳቤ ቢሆን ከእኔ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፣ ይልቁንም መጠየቅ የምትፈልገው ነገር ካለ ለምን በቀጥታ አትጠይቀኝም?" ሲል፣ ጠበቃዬ “ይህ መጀመሪያ ላይ ያነበቡት ደብዳቤ አቶ አማረ ለአልማዝ ከእንግዲህ ወዲህ እሱ ለእሷ ስለማይመጥን በፍቅር መቀጠል እንደማይፈልግና ይልቁንም ቢጤዋን ፈልጋ እንድታገባና የተሻለ ኑሮ እንድትኖር በመመኘት የጻፈውና ለመለያየታቸው መንስኤ ነው የተባለ ደብዳቤ ነው:: ሁለተኛው ደብዳቤ ደግሞ ወ/ት አልማዝ የጻፈችውና ከእሱ ጋር መቀጠል እንደማትችልና ሌላ ሚስት አግብቶ ቢኖር የተሻለ መሆኑን አስመልክቶ ጻፈችው የተባለ ደብዳቤ ነው፡፡ እንዲህ ይላል ብሎ ለችሎቱ ማንበብ ጀመረ፤ “ይድረስ ለውድ ጓደኛዬ ለአማረ አስረስ፡፡ በመጀመሪያ ለጤናህ እንደምን ሰንብተሃል:: እኔ እግዚአብሄር ይመስገን በጣሙን ደህና ነኝ:: ዛሬ የምጽፍልህን ይህን የመጨረሻ ደብዳቤዬን ስታነብ ትንሽም ቢሆን ማዘንህ እንደማይቀር እርግጠኛ ነኝ:: ነገር ግን የመጨረሻው ሐዘን ይበልጥ ሊከፋ ስለሚችል ከአሁኑ መወሰን ነበረብኝና መወሰኔ አልቀረም:: እንደምታውቀው አብረን ያሳለፍናቸው የፍቅር ዘመናት ለእኔም ሆነ ለአንተ እንዲህ በቀላሉ የሚረሱ አይደሉም:: ግን ይኼ ትዝታ መቆም እንዳለበት ተሰምቶኛል:: እንደምታውቀው እኔ በዚህ አለም ላይ ካንተ የተሻለ ዘመድም ሆነ መከታ ይኖረኛል ብዬ አልገምትም:: ለዚህም ነው አብረን በነበርንባቸው ጊዜያቶች ሁሉ አንተ ሁሌም አጠገቤ ስትሆን ደስታ፣ ስትርቀኝ ሐዘን ይፈራረቅብኝ የነበረው :: ይሁን እንጂ ጊዜ ግዜን እየወለደ ሲሄድ ሕይወትን በአሰብነው መንገድ ልንመራት አልቻልንም:: እሷ በፈለገችው መንገድ እየመራችን ሳንወድ በግድ መለያየታችን ቁርጥ ሆነ:: አሁንም ጊዜ ግዜን እየወለደ ሲሄድ የማይረሳ ነገር የለምና ሁሉም ነገር ሙሉ በሙሉ ባይረሳም እንደጥንቱ ግን ሊሆን አልቻለም። አሁን ስለፍቅር ወይም ስለትዳር ከማውራቴ በፊት ራሴን ማሸነፍ እንዳለብኝ እየተሰማኝ ነው:: መማር አለብኝ፡፡ ብዙ ነገር የማወቅ ፍላጎቴም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያየለ መጥቷል፡፡ ከዩንቨርስቲውም በጥሩ ውጤት ተመርቄ የዶ/ር አድማሱ እርዳታና አስተዋፅኦ ተጨምሮበት ዛሬ በትምህርቴ በጥሩ ደረጃ ላይ እገኛለሁ:: ከዚህ የሚበልጥ ትልቅ ነገር የለምና ይህንን
እንደጨረስኩ ለማስትሬቴም ለመማር ወስኜአለሁ:: ግን አንተ እኔን በመጠበቅ ሕይወትህ እንዲበላሽ አልሻም:: የራስህን ሕይወት በሚመስልህ መንገድ ብትመራ የተሻለ ነው፡፡ እኔ ከእንግዲህ ወዲያ አብዛኛውን ጊዜዬን በትምህርት ስለማላልፍ ያንተ ባለቤት ልሆን በምችልበት ደረጃ ላይ አይደለሁም:: የእኔን መጨረሻ እኔ ራሴም አላውቀውም:: ስለወደፊቱ ቃል ገብቼ ቃሌን ልጠብቅ አልጠብቅ እርግጠኛ ሳልሆን ላንተ ቃል መግባቱንም አልሻም:: የወደፊቱን የሚያውቀው ጌታ ብቻ ነውና:: ስለዚህ እኔ የራሴን ውሳኔ ወስኛለሁ:: ውሳኔዬንም በምድር ላይ ሊያስቀይረኝ የሚችል ኃይል ባለመኖሩ በዚህ በኩል እንዳትደክም እመክርሃለሁ:: ለጊዜው ላስከፋህ እንደምችል ባውቅም ወደፊት ግን ጥቅሙን ትረዳለህ ብዬ በማሰቤ በሥራዬ አልተፀፀትኩም:: ሁልጊዜ ላንተ ጥሩ ነገር በማሰቤ ሳላውቅ ላሳዝንህ ብችልም፣ አንተን ለመጉዳት ሆን ብዬ የማደርገው አይደለምና እንዳትቀየመኝ:: ከእንግዲህ ወዲያ ምንም ደብዳቤ ባትፅፍልኝ ደስ ይለኛል፡፡ የእኔን ሰላማዊ ሕይወት ከመረበሽ ውጪ የሚለውጠው ነገር የለምና አትድከም፡፡ የራስህን ምርጫ በጊዜ ውሰድ። በተረፈ ምን ጊዜም አልረሳህም:: ለአንተ ያለኝ ፍቅር እንዳለ እንዲቆይ ከፈለግህም _ ሃሳቤን ለማስለወጥ አትሞክር፡፡ ሁሌ የማይለይህ አምላክ ክአንተ ጋር ይሁን፡፡ ውድ ጓደኛህ አልማዝ ታፈሰ" ብሎ አንብቦ እንደጨረሰ ጥያቄ ለመጠየቅ ሲዘጋጅ፣ ዶ/ሩ ከአፉ ነጥቆ፤ “ታዲያ ይህ እኔን ምን ይመለከታል? ከእኔ ጋር ባልተያያዘ ነገር ነው ጊዜዬን የምታጠፋው" አለ። በይግባኙ ወቅት አዳዲሶቹ ተጨማሪ ማስረጃዎች ለፍ/ቤቱና ለአቃቤ ሕጉ ቀርበው ስለነበር ወረቀቶቹ እዚያም ቢሆን ተነበው ይዘታቸው ታውቋልና ጠበቃዬ ፈገግ እንደማለት ብሎ፤ "ዶ/ር፧ እርሶም እንዳዩት ሁለቱም ደብዳቤዎች ተመሳሳይ ናቸው፡፡ በመጀመሪያው አቶ አማረ ጻፈው በተባለው ደብዳቤ ውስጥ ለመለያየታቸው እንደምክንያት በሟች ዲያሪ ውስጥ የተጻፈው አቶ አማረ ቢጤውን ለማግባት መወሰኑ ሲሆን፤ በዚህ ደብዳቤ ደግሞ ለመለያየታቸው ምክንያቱ ሟች ትምህርቷን መቀጠል መፈለጓ ከመሆኑ በስተቀር ደብዳቤው እምብዛም ልዩነት አልነበረውም። ከዚህ በላይ ደግሞ ሁለቱም ደብዳቤዎች ላይ ያለው የእጅ ጽሑፍ ተመሳሳይ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ደብዳቤዎቹ ያለ ጥርጥር ከእርሶ ውጪ በማንም እንዳልተጻፉ ለእርሶም ሆነ ለማንም ትክክለኛ ጉዳይ አጣሪና ለሐሰት አሳዳጅ ሰው ግልጽ ነው፡፡" ሲል ዶ/ር አድማሱ ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ፧
“በፍፁም ሀሰት ነው! ሀስት ነው!' እያለ ጮኸ፡፡ ፍርዱን ሲከታተል የነበረው ሁሉ ያልጠበቀውን ነገር በመስማቱ እርስ በእርሱ የሹክሹክታ ወሬ ጀመረ፡፡ እነሆ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ሁሉ ዘመን ሲያስጨንቀኝ የነበረውና ያንን ሁሉ ገጽ ሳነብ ልፈታው ያልቻልኩት እንቆቅልሽ ተፈታ:: በንዴትም ሳላስበው "ወይኔ! ወይኔ! ወይኔ! ሰውየው፤ ቆይ አገኝሀለሁ!'' ብዬ ጮህኩ፡፡ ሳላስበው ተጨማሪ ወንጀል እየፈፀምኩ መሆኔን እንኳን ማሰብ ተስኖኝ ነበር:: ዳኛው በንዴት ሥነሥርዓት በማለት ጠረጴዛውን በያዙት መዶሻ መታቱት:: ዶ/ር አድማሱ ግን እየደጋገመ “ሀሰት ነው'' አያለ ሲጮህ ጠበቃዬ! “ዶ/ር አድማሱ "አጉል መፍጨርጨር ለመላላጥ ነው" እንደሚባለው እውነቱን ለማስተባበል ባይሞክሩ ጥሩ ነው፡፡ ይኸ የእርሶ የእጅ ጽሑፍ እንደሆነ በአባዲና ፖሊስ ምርመራ ተረጋግጧል” ሲል፣ አቃቤ ሕግ ተስፋ በመቁረጥ አንገቱን ደፋ፡፡ ጠበቃዬ ዶ/ሩ እንዲረጋጋ ይመስላል ጥያቄውን ለአፍታ ያህል ቆም በማድረግ ፋታ ከሰጠውና ፊቱን በመሀረብ ጠርጎ መጨረሱን ከተመለከተ በኋላ ሌላ አንድ ደብዳቤ አውጥቶ በችሎቱ በኩል አሰጠው:: ዶ/ሩ ደብዳቤውን አንብቦ እንደጨረሰ፤ “እና ታዲያ ምን ላድርገው? ይኼ የእኔ የእጅ ጽሑፍ አይደለም፤ የአልማዝ የእጅ ጸሑፍ ነው” አለ፡፡ “አዎ ልክ ነዎት፤ ይህ ጽሑፍ የእርስዎ የእጅ ጽሑፍ ሳይሆን የአልማዝ የእጅ ጽሑፍ ነው:: በዚህ እሷ ጻፈችው በተባለውና እርሶ በጻፉት ደብዳቤ መካከል ያለው ልዩነት ግልፅ ነው፡፡ ይህንንም እርሶም እያረጋገጡት ነውና ክርክሩን አቁመው ይልቁንም ይህ አልማዝ እራሷን እንደገደለች የሚገልፅውን ደብዳቤ እንዴት እንደጻፈችው ቢገልፁልን የተሻለ ነው” ሲል ጠየቀ
እና ይህ ደብዳቤ ከእኔ ጋር ምን ያገናኘዋል?'' በማለት ጮኸ ተናገረ:: ጠበቃዬ መልስ ሳይሰጥ በተረጋጋ መልኩ ሌላ ደብዳቤ እንዲሰጠው አደረገ፡፡ ዶ/ሩ ወረቀቱን እንደያዘ ጠበቃዬንና ዳኞቹን በየተራ አያቸው:: ፊቲ በላብ ተደፍቆ ደብዳቤውን ማንበብ ተያያዘው:: እንደጨረሰም : “ይህም ደብዳቤ ቢሆን ከእኔ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፣ ይልቁንም መጠየቅ የምትፈልገው ነገር ካለ ለምን በቀጥታ አትጠይቀኝም?" ሲል፣ ጠበቃዬ “ይህ መጀመሪያ ላይ ያነበቡት ደብዳቤ አቶ አማረ ለአልማዝ ከእንግዲህ ወዲህ እሱ ለእሷ ስለማይመጥን በፍቅር መቀጠል እንደማይፈልግና ይልቁንም ቢጤዋን ፈልጋ እንድታገባና የተሻለ ኑሮ እንድትኖር በመመኘት የጻፈውና ለመለያየታቸው መንስኤ ነው የተባለ ደብዳቤ ነው:: ሁለተኛው ደብዳቤ ደግሞ ወ/ት አልማዝ የጻፈችውና ከእሱ ጋር መቀጠል እንደማትችልና ሌላ ሚስት አግብቶ ቢኖር የተሻለ መሆኑን አስመልክቶ ጻፈችው የተባለ ደብዳቤ ነው፡፡ እንዲህ ይላል ብሎ ለችሎቱ ማንበብ ጀመረ፤ “ይድረስ ለውድ ጓደኛዬ ለአማረ አስረስ፡፡ በመጀመሪያ ለጤናህ እንደምን ሰንብተሃል:: እኔ እግዚአብሄር ይመስገን በጣሙን ደህና ነኝ:: ዛሬ የምጽፍልህን ይህን የመጨረሻ ደብዳቤዬን ስታነብ ትንሽም ቢሆን ማዘንህ እንደማይቀር እርግጠኛ ነኝ:: ነገር ግን የመጨረሻው ሐዘን ይበልጥ ሊከፋ ስለሚችል ከአሁኑ መወሰን ነበረብኝና መወሰኔ አልቀረም:: እንደምታውቀው አብረን ያሳለፍናቸው የፍቅር ዘመናት ለእኔም ሆነ ለአንተ እንዲህ በቀላሉ የሚረሱ አይደሉም:: ግን ይኼ ትዝታ መቆም እንዳለበት ተሰምቶኛል:: እንደምታውቀው እኔ በዚህ አለም ላይ ካንተ የተሻለ ዘመድም ሆነ መከታ ይኖረኛል ብዬ አልገምትም:: ለዚህም ነው አብረን በነበርንባቸው ጊዜያቶች ሁሉ አንተ ሁሌም አጠገቤ ስትሆን ደስታ፣ ስትርቀኝ ሐዘን ይፈራረቅብኝ የነበረው :: ይሁን እንጂ ጊዜ ግዜን እየወለደ ሲሄድ ሕይወትን በአሰብነው መንገድ ልንመራት አልቻልንም:: እሷ በፈለገችው መንገድ እየመራችን ሳንወድ በግድ መለያየታችን ቁርጥ ሆነ:: አሁንም ጊዜ ግዜን እየወለደ ሲሄድ የማይረሳ ነገር የለምና ሁሉም ነገር ሙሉ በሙሉ ባይረሳም እንደጥንቱ ግን ሊሆን አልቻለም። አሁን ስለፍቅር ወይም ስለትዳር ከማውራቴ በፊት ራሴን ማሸነፍ እንዳለብኝ እየተሰማኝ ነው:: መማር አለብኝ፡፡ ብዙ ነገር የማወቅ ፍላጎቴም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያየለ መጥቷል፡፡ ከዩንቨርስቲውም በጥሩ ውጤት ተመርቄ የዶ/ር አድማሱ እርዳታና አስተዋፅኦ ተጨምሮበት ዛሬ በትምህርቴ በጥሩ ደረጃ ላይ እገኛለሁ:: ከዚህ የሚበልጥ ትልቅ ነገር የለምና ይህንን
እንደጨረስኩ ለማስትሬቴም ለመማር ወስኜአለሁ:: ግን አንተ እኔን በመጠበቅ ሕይወትህ እንዲበላሽ አልሻም:: የራስህን ሕይወት በሚመስልህ መንገድ ብትመራ የተሻለ ነው፡፡ እኔ ከእንግዲህ ወዲያ አብዛኛውን ጊዜዬን በትምህርት ስለማላልፍ ያንተ ባለቤት ልሆን በምችልበት ደረጃ ላይ አይደለሁም:: የእኔን መጨረሻ እኔ ራሴም አላውቀውም:: ስለወደፊቱ ቃል ገብቼ ቃሌን ልጠብቅ አልጠብቅ እርግጠኛ ሳልሆን ላንተ ቃል መግባቱንም አልሻም:: የወደፊቱን የሚያውቀው ጌታ ብቻ ነውና:: ስለዚህ እኔ የራሴን ውሳኔ ወስኛለሁ:: ውሳኔዬንም በምድር ላይ ሊያስቀይረኝ የሚችል ኃይል ባለመኖሩ በዚህ በኩል እንዳትደክም እመክርሃለሁ:: ለጊዜው ላስከፋህ እንደምችል ባውቅም ወደፊት ግን ጥቅሙን ትረዳለህ ብዬ በማሰቤ በሥራዬ አልተፀፀትኩም:: ሁልጊዜ ላንተ ጥሩ ነገር በማሰቤ ሳላውቅ ላሳዝንህ ብችልም፣ አንተን ለመጉዳት ሆን ብዬ የማደርገው አይደለምና እንዳትቀየመኝ:: ከእንግዲህ ወዲያ ምንም ደብዳቤ ባትፅፍልኝ ደስ ይለኛል፡፡ የእኔን ሰላማዊ ሕይወት ከመረበሽ ውጪ የሚለውጠው ነገር የለምና አትድከም፡፡ የራስህን ምርጫ በጊዜ ውሰድ። በተረፈ ምን ጊዜም አልረሳህም:: ለአንተ ያለኝ ፍቅር እንዳለ እንዲቆይ ከፈለግህም _ ሃሳቤን ለማስለወጥ አትሞክር፡፡ ሁሌ የማይለይህ አምላክ ክአንተ ጋር ይሁን፡፡ ውድ ጓደኛህ አልማዝ ታፈሰ" ብሎ አንብቦ እንደጨረሰ ጥያቄ ለመጠየቅ ሲዘጋጅ፣ ዶ/ሩ ከአፉ ነጥቆ፤ “ታዲያ ይህ እኔን ምን ይመለከታል? ከእኔ ጋር ባልተያያዘ ነገር ነው ጊዜዬን የምታጠፋው" አለ። በይግባኙ ወቅት አዳዲሶቹ ተጨማሪ ማስረጃዎች ለፍ/ቤቱና ለአቃቤ ሕጉ ቀርበው ስለነበር ወረቀቶቹ እዚያም ቢሆን ተነበው ይዘታቸው ታውቋልና ጠበቃዬ ፈገግ እንደማለት ብሎ፤ "ዶ/ር፧ እርሶም እንዳዩት ሁለቱም ደብዳቤዎች ተመሳሳይ ናቸው፡፡ በመጀመሪያው አቶ አማረ ጻፈው በተባለው ደብዳቤ ውስጥ ለመለያየታቸው እንደምክንያት በሟች ዲያሪ ውስጥ የተጻፈው አቶ አማረ ቢጤውን ለማግባት መወሰኑ ሲሆን፤ በዚህ ደብዳቤ ደግሞ ለመለያየታቸው ምክንያቱ ሟች ትምህርቷን መቀጠል መፈለጓ ከመሆኑ በስተቀር ደብዳቤው እምብዛም ልዩነት አልነበረውም። ከዚህ በላይ ደግሞ ሁለቱም ደብዳቤዎች ላይ ያለው የእጅ ጽሑፍ ተመሳሳይ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ደብዳቤዎቹ ያለ ጥርጥር ከእርሶ ውጪ በማንም እንዳልተጻፉ ለእርሶም ሆነ ለማንም ትክክለኛ ጉዳይ አጣሪና ለሐሰት አሳዳጅ ሰው ግልጽ ነው፡፡" ሲል ዶ/ር አድማሱ ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ፧
“በፍፁም ሀሰት ነው! ሀስት ነው!' እያለ ጮኸ፡፡ ፍርዱን ሲከታተል የነበረው ሁሉ ያልጠበቀውን ነገር በመስማቱ እርስ በእርሱ የሹክሹክታ ወሬ ጀመረ፡፡ እነሆ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ሁሉ ዘመን ሲያስጨንቀኝ የነበረውና ያንን ሁሉ ገጽ ሳነብ ልፈታው ያልቻልኩት እንቆቅልሽ ተፈታ:: በንዴትም ሳላስበው "ወይኔ! ወይኔ! ወይኔ! ሰውየው፤ ቆይ አገኝሀለሁ!'' ብዬ ጮህኩ፡፡ ሳላስበው ተጨማሪ ወንጀል እየፈፀምኩ መሆኔን እንኳን ማሰብ ተስኖኝ ነበር:: ዳኛው በንዴት ሥነሥርዓት በማለት ጠረጴዛውን በያዙት መዶሻ መታቱት:: ዶ/ር አድማሱ ግን እየደጋገመ “ሀሰት ነው'' አያለ ሲጮህ ጠበቃዬ! “ዶ/ር አድማሱ "አጉል መፍጨርጨር ለመላላጥ ነው" እንደሚባለው እውነቱን ለማስተባበል ባይሞክሩ ጥሩ ነው፡፡ ይኸ የእርሶ የእጅ ጽሑፍ እንደሆነ በአባዲና ፖሊስ ምርመራ ተረጋግጧል” ሲል፣ አቃቤ ሕግ ተስፋ በመቁረጥ አንገቱን ደፋ፡፡ ጠበቃዬ ዶ/ሩ እንዲረጋጋ ይመስላል ጥያቄውን ለአፍታ ያህል ቆም በማድረግ ፋታ ከሰጠውና ፊቱን በመሀረብ ጠርጎ መጨረሱን ከተመለከተ በኋላ ሌላ አንድ ደብዳቤ አውጥቶ በችሎቱ በኩል አሰጠው:: ዶ/ሩ ደብዳቤውን አንብቦ እንደጨረሰ፤ “እና ታዲያ ምን ላድርገው? ይኼ የእኔ የእጅ ጽሑፍ አይደለም፤ የአልማዝ የእጅ ጸሑፍ ነው” አለ፡፡ “አዎ ልክ ነዎት፤ ይህ ጽሑፍ የእርስዎ የእጅ ጽሑፍ ሳይሆን የአልማዝ የእጅ ጽሑፍ ነው:: በዚህ እሷ ጻፈችው በተባለውና እርሶ በጻፉት ደብዳቤ መካከል ያለው ልዩነት ግልፅ ነው፡፡ ይህንንም እርሶም እያረጋገጡት ነውና ክርክሩን አቁመው ይልቁንም ይህ አልማዝ እራሷን እንደገደለች የሚገልፅውን ደብዳቤ እንዴት እንደጻፈችው ቢገልፁልን የተሻለ ነው” ሲል ጠየቀ
። ዶ/ሩ ከዚህ በላይ እውነትን መጋፈጥ እንዳቃተው ፊቱ ላይ ይነበባል፡፡ ወጥመድ ውስጥ የገባች አይጥ ሆኖ ግራ ቀኙን ቢያይ ምንም ማምለጪያ እንደሌለው አወቀ፡፡ ፊቱ ይበልጥ ፍም መሰለ፡፡ ለጥቂት ሴኮንዶች በዝምታ ከተዋጠ በኋላ፣ ንዴት በተናነቀው ሁኔታ ድምፁን ሁሉም እስኪሰማው ከፍ አድርጎ፤ “አዎ ገድያታለሁ" አለ፡፡ ችሎቱ በአንድ ጊዜ በታዳሚው ጫጫታ ታወከ፡፡
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
🍁🍁ዲያሪው 📝
ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_22
“አዎ ገድያታለሁ!" አለ፡፡ ችሎቱ በአንድ ጊዜ በታዳሚው ጫጫታ ታወከ፡፡ እኔ ፍጹም ያልጠበቅሁትን ነገር በመስማቴ በቁሜ ደረቅሁ፡፡ ዳኛው በመዶሻቸው ፀጥታውን አስከበሩ፡፡ ጠበቃዬም፤
"ይህንንማ አውቄዋለሁ፤ ግን ለምን?" ሲለው፡፡ ፊቱ ላይ አንዳችም የመፀፀት ስሜት ሳይታይበት፤ "ለእሷ ሞት ያንሳት እንደሆነ እንጂ የሚበዛባት አይደለም:: አሁንም ሁለተኛ ተነስታ ዳግመኛ ብገድላት እንኳን በእኔ ላይ የፈፀመቺውን በደል የሚያካክስ አይደለም:: ከሁሉ አስበልጬ እየወደድኳት፣ እሷን አጥቼ መኖር እንደማልችል እያወቀች፣ ፍቅሬን ረግጣው ለመሄድ ሞከረች:: ከራሴ በላይ እሷን የተሻለች ሰው ለማድረግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል ለጥሩ ነገር ላበቃት ብችልም የእኔ ድካም፣ የእኔ ውለታ፣ ለእሷ ምንም አልነበረም:: ሁሌ ጊዜ ከእኔ ይልቅ የምትናፍቀው ይህንን ደደብ ነበር:: ዳሩ ግን እሷ የእናትነትና የአባትነት ፍቅርን አይታ ስለማታውቅ ለፍቅር ስለፍቅር የሚያስብ ህሊና አልነበራትምና አልፈርድባትም:: እኔ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ አንድ ቀን ታፈቅረኝ ይሆናል እያልኩ የቻልኩትን ሁሉ ብጥርም እሷ ግን ለእኔ በድኗን እንጂ መንፈሷን ሳትሰጠኝ ለሶስት ዓመታት በአንድ ቤት ውስጥ አብረን የይስሙላ ህይወት ኖርን:: ይህ ሁሉ ሆኖ ግን አንድ ቀን ትወደኝ ይሆናል፣ ልጅ ስንወልድ ታፈቅረኝ ይሆናል እያልኩ ተስፋ ሳልቆርጥ በእሷ የምወደድበትን ቀን በናፍቆት መጠባበቁን ተያያዝኩት:: ግን ምን ያደርጋል! ልፋቴ ሁሉ የእምቧይ ካብ ነበር፡፡ ምንም ያህል ብጥር፣ ምንም ያህል ጥሩ ነገር ብሰራ ሕሊናዋ ውስጥ አልገባ አልኩኝ። በእሷ አባባል እኔን በወንድምነት እንጂ በፍቅር ሊቀበል የሚችል ልቦና አልነበራትም፡፡ ወሬዋ ሁሉ ስለአማረ ነበር፡፡ ዓይኖችዋ ማየት የሚፈልጉትና የሚመኙት እኔን ሳይሆን በእኔ ውስጥ አሻግረው የሚያዩት እሱኑ ነበር። ሌላው ቀርቶ አልጋ ላይ በፍቅር ጨዋታ ወቅት የምትጠራው የእኔን ስም ሳይሆን የእሱን ስም ነበር፡፡ የእኔ የራሴ ብቻ ላደርጋት የወስንኩትን ሁሉ እንደፈላ ውኃ አተነነችው፡፡ይህ ደግሞ እጅግ በጣም አተከነኝ:: ስለዚህ ቀናሁ፡፡ ለዚህ ደግሞ ብቸኛው መፍትሄ አሷን ከእሱ ጋር ማለያየት ብቻ ነው ብዬ ስላሰብኩ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አንድ መላ ፈጠርኩ። በመጀመሪያ ቢያንስ እሷ ደብዳቤ እየጻፈችለት እሱ መልስ የማይሰጥ ከሆነ ተስፋ ቆርጣ ትተወው ይሆናል ብዬ ስላሰብኩ አማረ የሚጽፋቸውን ደብዳቤዎች ከፖስታ ቤት ሳጥናችን ውስጥ ቀድሜ እያወጣሁ ማቃጠሉን ተያያዝኩት፡፡ በተቻለ መጠንም እንዳይደርሳት አደረኩ፡፡ እሷ ግን ተስፋ ባለመቁረጥ ትጽፍለት ነበር፡፡ "ባይመቸው ነው እንጂ ሲመቸው ይጽፍልኝ ይሆናል" እያለች በተደጋጋሚ ትሞክር ነበር። በመጨረሻ ግን ሌላ አማራጭ መፈለግ ነበረብኝና እነዚህ የምታሳየኝን ሁለቱም ተስፋ ያስቆርጣሉ ያልኳቸውን ደብዳቤዎች ጽፌ በእሱና በእሷ ስም በተለያየ ጊዜ አሽጌ ላኩኝ፡፡ ይህንንም እንዳታውቅብኝ የተቻለኝን ሁሉ
አደረኩ፡፡ ይኸ በእርግጥ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ተሳክቶልኛል፡፡ እሷም ሆነች እሱ ድርጊቱን በእውነትነት ስለተቀበሉት ሁለቱም ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓቸዋል፡፡ ነገር ግን ይህም ቢሆን ሊዘልቅ አልቻለም፡፡ እንዴት ልታውቅ እንደቻለች ባይገባኝም ወደ መጨረሻ አካባቢ ሁለቱም ደብዳቤዎች በእኒ እንደተጻፉ በማወቋ ይበልጥ ጠላችኝ፡፡ ይህንን ሁሉ ያደረግሁት ለፍቅሯ ስልና እጅግ በጣም ስለምወዳት ነበር። እሷን ለማንም ቢሆን አሳልፌ መስጠትን ህሊናዬ የሚቀበለው ጉዳይ አልነበረምና እውነታውን ተቀብዬ አርፌ መቀመጥ አልቻኩም:: ልቤን ሰብሮ እጅግ ተስፋ ያስቆረጥኝ ግን ዘወትር በምታነበው መጽሐፏ ውስጥ ያገኘሁት የደብዳቤ ረቂቅ ነበር፡፡ ተጽፎ ያልተላከውን ለጓደኛዋ ኤልሳ የተጻፈውን ደብዳቤ እንዳነበብኩ ክፉኛ አንቀጠቀጠኝ፤ አሁንም ቢሆን ያንገሸግሸኛል፡፡ ኮፒውን አስቀርቼ ደጋግሜ ስላነበብኩት በቃሌ አጥንቼዋለሁ ማለት ይቻላል፡፡ እንዲህ እኳ ነው ያለችኝ፡፡ "ዶ/ር አድማሱ ራስ ወዳድ ነው፡፡ እኔ ለእሱ ከወንድምነት ያለፈ ፍቅር እንደሌለኝና መቼም ቢሆን የእሱ ዘላቂ ፍቅረኛ ልሆን እንደማልችል እያወቀ ለእኔ ደስታ ሳያስብ ለራሱ ፍላጎት ብቻ በመጨነቅ የእኔ ሕይወት አበላሽቶ በእኔ መደሰት መፈለጉን ሳስብ ይበልጥ እንድጠላው ያደርገኛል:: እኔ ለአማረ፣ አማረ ለእኔ ምን ያህል ፍቅር እንዳለን እያወቀና በሚያደርገው እኩይ ተግባር ሁለታችንም ምን ያህል ልንጎዳ እንደምንችል እየተገነዘበ፣ በሁለታችን ደስታ ማጣት የራሱን ደስታ ለመግዛት ሲሞክር ማየት ምንጊዜም ቢሆን የሚያናድድ ተግባር ነው:: በዚህም የተነሳ ለእኔ ከእሱ ጋር ተመልሶ አብሮ መኖር ቀርቶ ማሰቡም ሆነ መሞከሩ ራሱ የማይቻል ሁኔታ ነው፡፡ እርግጥ ነው ዶ/ር አድማሱ፣ ለእኔ ያለውን ፍቅርና በዚህም የተነሳ ያደረገልኝን ነገር ሁሉ ምንግዜም የምረሳው አይደለም:: በልቤ ውስጥ ትልቅ ቦታ አለው:: አንድ የምተማመንበት ዘመዴ እሱ ነው ብዬ ስላመንኩ ሳላቅማማ ያለኝን ሁሉንም ነገር አሳልፌ ልሰጠው ሞከርኩ፡፡ ግን ገላዬን እንጂ ጥልቅ ፍቅሬን ልሰጠው አልቻልኩም፡፡ ውጪያዊ አካሌ እንጂ ነፍሴ ከሱ ጋር ልትሆን አልቃጣችም:: በተለይ አሁን ከአማረ ጋር እንዴት እንደተለያየን ካወቅሁ በኋላና ያለ በደሉ በደለኛ አድርጌ መለያየቴን ስገነዘብ ፀፀቱ በፍጹም አላስቀምጥ አለኝ፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ እስካሁን አላግባብ ሳብጠለጥለው መኖሬን ሳስብና ከሁሉም በላይ ደግሞ ዶ/ር አድማሱ ያደረገውን ነገር ሁሉ እያወቅሁ፣ በምንም ተአምር ተመልሼ የእሱ ፍቅረኛ ሆኜ ልኖር እንደማልችል ይታየኛል፡፡ አርግጥ እሱ ለእኔ ካለው ፍቅር የተነሳ ያደረገው መሆኑን ስለማውቅ ጥፋቱን ሁሉ ይቅር ልለው እችላለሁ፣ ሆኖም እላይ
በጠቀስካቸው ምክንያቶች የተነሳ ዳግም የእሱ ፍቅረኛ ለመሆን ግን በምንም ሁኔታ አይቻለኝም:: የበደልኩትን ፍቅረኛዬን ፈልጌና እግሩ ላይ ወድቂ ይቅርታ ለመጠየቅ ወደ አንቺ እየመጣሁ ነው:: ቢያንስ ዳግም ባያፈቅረኝ እንኳ ይቅር ካለኝ ይበቃኛል" ይላል፡፡ ይህንን ደብዳቤ እንዳነበብኩ ራሴን መቆጣጠር ተሳነኝ፡ ከጽሑፉ ምሬት የተነሳ ሳልወድ በግድ ደጋግሜ አነበብኩት፤ በቃሌም አጠናሁት፡፡ ይህን በሕልሜም በውኔም ይሆናል ብዬ ያልጠበኩትን ነገር በራሷ የእጅ ጽሑፍ ሳነብ ውስጤ እሳት የተለኮሰበት ያህል ነደደ፡፡ ግን መጨከን አልቻልኩም፡፡ በዚሁ የተነሳ ጥላኝ ለመሄድ በተነሳችበት ዕለት ጨክኜ ላሰናብታት አልቻልኩም፡፡ ጽኑ ፍቅሬን እየገለጽኩላትና የወደፊቱን አስደሳች የሚሆን ሕይወታችንን በልዩ ልዩ መልክ እያብራራሁላት እንድትቀር ለመንኳት፡፡ እሷ ግን እምነቴንና ተስፋዬንም በእሷ ላይ ማሳደሬን በተደጋጋሚ ነግሬያት ሳለ ታደርገዋለች ብዬ በሙሉ ልቤ ሳላምን ጥላኝ ሄደች፡፡ ይህንን ሁሉ ውለታና ለእሷ ያለኝን ፍቅር ከምንም ሳትቆጥር ጥላኝ ወደ እዚህ እርኩስ ለመሄድ ወሰነች:: ለመንኳት፣ እግሯ ላይ ተንበርክኬ ቅሪ እያልኩ እያለቀስኩ ተማፀንኳት፣ ከእሷ ወዲያ ሕይወት ለእኔ ትርጉም እንደሌለው እና በእኔ ላይ በምትፈፅመው ነገር የኋላ ኋላ ከምትፀፀት ብትቀር እንደሚሻል ደጋግሜ ነገርኳት፡፡ አንጀት ካላት በማለት እንድትራራልኝ ጣርኩ፡፡ ለእሷ ግን ይህ ሁሉ መማፀን ምንም ዋጋ አልነበረውም:: እነዚህ ሁለት ደብዳቤዎች በእኔ መጻፋቸውን በማወቋ እጅግ አድርጋ ጠላቺኝ:: አፍ አውጥታ ለምን ይህንን እንዳደረኩ ግን ልትጠይቀኝ አልፈለገችም፡፡ ነገር ግን ይህ ድርጊቴም ቢሆን በእኔ ላይ እንዲህ የከፋ ጥላቻን ሊያስከትል የሚችል መሆን አልነበረበትም:: ምንም
ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_22
“አዎ ገድያታለሁ!" አለ፡፡ ችሎቱ በአንድ ጊዜ በታዳሚው ጫጫታ ታወከ፡፡ እኔ ፍጹም ያልጠበቅሁትን ነገር በመስማቴ በቁሜ ደረቅሁ፡፡ ዳኛው በመዶሻቸው ፀጥታውን አስከበሩ፡፡ ጠበቃዬም፤
"ይህንንማ አውቄዋለሁ፤ ግን ለምን?" ሲለው፡፡ ፊቱ ላይ አንዳችም የመፀፀት ስሜት ሳይታይበት፤ "ለእሷ ሞት ያንሳት እንደሆነ እንጂ የሚበዛባት አይደለም:: አሁንም ሁለተኛ ተነስታ ዳግመኛ ብገድላት እንኳን በእኔ ላይ የፈፀመቺውን በደል የሚያካክስ አይደለም:: ከሁሉ አስበልጬ እየወደድኳት፣ እሷን አጥቼ መኖር እንደማልችል እያወቀች፣ ፍቅሬን ረግጣው ለመሄድ ሞከረች:: ከራሴ በላይ እሷን የተሻለች ሰው ለማድረግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል ለጥሩ ነገር ላበቃት ብችልም የእኔ ድካም፣ የእኔ ውለታ፣ ለእሷ ምንም አልነበረም:: ሁሌ ጊዜ ከእኔ ይልቅ የምትናፍቀው ይህንን ደደብ ነበር:: ዳሩ ግን እሷ የእናትነትና የአባትነት ፍቅርን አይታ ስለማታውቅ ለፍቅር ስለፍቅር የሚያስብ ህሊና አልነበራትምና አልፈርድባትም:: እኔ ግን ተስፋ ሳልቆርጥ አንድ ቀን ታፈቅረኝ ይሆናል እያልኩ የቻልኩትን ሁሉ ብጥርም እሷ ግን ለእኔ በድኗን እንጂ መንፈሷን ሳትሰጠኝ ለሶስት ዓመታት በአንድ ቤት ውስጥ አብረን የይስሙላ ህይወት ኖርን:: ይህ ሁሉ ሆኖ ግን አንድ ቀን ትወደኝ ይሆናል፣ ልጅ ስንወልድ ታፈቅረኝ ይሆናል እያልኩ ተስፋ ሳልቆርጥ በእሷ የምወደድበትን ቀን በናፍቆት መጠባበቁን ተያያዝኩት:: ግን ምን ያደርጋል! ልፋቴ ሁሉ የእምቧይ ካብ ነበር፡፡ ምንም ያህል ብጥር፣ ምንም ያህል ጥሩ ነገር ብሰራ ሕሊናዋ ውስጥ አልገባ አልኩኝ። በእሷ አባባል እኔን በወንድምነት እንጂ በፍቅር ሊቀበል የሚችል ልቦና አልነበራትም፡፡ ወሬዋ ሁሉ ስለአማረ ነበር፡፡ ዓይኖችዋ ማየት የሚፈልጉትና የሚመኙት እኔን ሳይሆን በእኔ ውስጥ አሻግረው የሚያዩት እሱኑ ነበር። ሌላው ቀርቶ አልጋ ላይ በፍቅር ጨዋታ ወቅት የምትጠራው የእኔን ስም ሳይሆን የእሱን ስም ነበር፡፡ የእኔ የራሴ ብቻ ላደርጋት የወስንኩትን ሁሉ እንደፈላ ውኃ አተነነችው፡፡ይህ ደግሞ እጅግ በጣም አተከነኝ:: ስለዚህ ቀናሁ፡፡ ለዚህ ደግሞ ብቸኛው መፍትሄ አሷን ከእሱ ጋር ማለያየት ብቻ ነው ብዬ ስላሰብኩ ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አንድ መላ ፈጠርኩ። በመጀመሪያ ቢያንስ እሷ ደብዳቤ እየጻፈችለት እሱ መልስ የማይሰጥ ከሆነ ተስፋ ቆርጣ ትተወው ይሆናል ብዬ ስላሰብኩ አማረ የሚጽፋቸውን ደብዳቤዎች ከፖስታ ቤት ሳጥናችን ውስጥ ቀድሜ እያወጣሁ ማቃጠሉን ተያያዝኩት፡፡ በተቻለ መጠንም እንዳይደርሳት አደረኩ፡፡ እሷ ግን ተስፋ ባለመቁረጥ ትጽፍለት ነበር፡፡ "ባይመቸው ነው እንጂ ሲመቸው ይጽፍልኝ ይሆናል" እያለች በተደጋጋሚ ትሞክር ነበር። በመጨረሻ ግን ሌላ አማራጭ መፈለግ ነበረብኝና እነዚህ የምታሳየኝን ሁለቱም ተስፋ ያስቆርጣሉ ያልኳቸውን ደብዳቤዎች ጽፌ በእሱና በእሷ ስም በተለያየ ጊዜ አሽጌ ላኩኝ፡፡ ይህንንም እንዳታውቅብኝ የተቻለኝን ሁሉ
አደረኩ፡፡ ይኸ በእርግጥ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ተሳክቶልኛል፡፡ እሷም ሆነች እሱ ድርጊቱን በእውነትነት ስለተቀበሉት ሁለቱም ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓቸዋል፡፡ ነገር ግን ይህም ቢሆን ሊዘልቅ አልቻለም፡፡ እንዴት ልታውቅ እንደቻለች ባይገባኝም ወደ መጨረሻ አካባቢ ሁለቱም ደብዳቤዎች በእኒ እንደተጻፉ በማወቋ ይበልጥ ጠላችኝ፡፡ ይህንን ሁሉ ያደረግሁት ለፍቅሯ ስልና እጅግ በጣም ስለምወዳት ነበር። እሷን ለማንም ቢሆን አሳልፌ መስጠትን ህሊናዬ የሚቀበለው ጉዳይ አልነበረምና እውነታውን ተቀብዬ አርፌ መቀመጥ አልቻኩም:: ልቤን ሰብሮ እጅግ ተስፋ ያስቆረጥኝ ግን ዘወትር በምታነበው መጽሐፏ ውስጥ ያገኘሁት የደብዳቤ ረቂቅ ነበር፡፡ ተጽፎ ያልተላከውን ለጓደኛዋ ኤልሳ የተጻፈውን ደብዳቤ እንዳነበብኩ ክፉኛ አንቀጠቀጠኝ፤ አሁንም ቢሆን ያንገሸግሸኛል፡፡ ኮፒውን አስቀርቼ ደጋግሜ ስላነበብኩት በቃሌ አጥንቼዋለሁ ማለት ይቻላል፡፡ እንዲህ እኳ ነው ያለችኝ፡፡ "ዶ/ር አድማሱ ራስ ወዳድ ነው፡፡ እኔ ለእሱ ከወንድምነት ያለፈ ፍቅር እንደሌለኝና መቼም ቢሆን የእሱ ዘላቂ ፍቅረኛ ልሆን እንደማልችል እያወቀ ለእኔ ደስታ ሳያስብ ለራሱ ፍላጎት ብቻ በመጨነቅ የእኔ ሕይወት አበላሽቶ በእኔ መደሰት መፈለጉን ሳስብ ይበልጥ እንድጠላው ያደርገኛል:: እኔ ለአማረ፣ አማረ ለእኔ ምን ያህል ፍቅር እንዳለን እያወቀና በሚያደርገው እኩይ ተግባር ሁለታችንም ምን ያህል ልንጎዳ እንደምንችል እየተገነዘበ፣ በሁለታችን ደስታ ማጣት የራሱን ደስታ ለመግዛት ሲሞክር ማየት ምንጊዜም ቢሆን የሚያናድድ ተግባር ነው:: በዚህም የተነሳ ለእኔ ከእሱ ጋር ተመልሶ አብሮ መኖር ቀርቶ ማሰቡም ሆነ መሞከሩ ራሱ የማይቻል ሁኔታ ነው፡፡ እርግጥ ነው ዶ/ር አድማሱ፣ ለእኔ ያለውን ፍቅርና በዚህም የተነሳ ያደረገልኝን ነገር ሁሉ ምንግዜም የምረሳው አይደለም:: በልቤ ውስጥ ትልቅ ቦታ አለው:: አንድ የምተማመንበት ዘመዴ እሱ ነው ብዬ ስላመንኩ ሳላቅማማ ያለኝን ሁሉንም ነገር አሳልፌ ልሰጠው ሞከርኩ፡፡ ግን ገላዬን እንጂ ጥልቅ ፍቅሬን ልሰጠው አልቻልኩም፡፡ ውጪያዊ አካሌ እንጂ ነፍሴ ከሱ ጋር ልትሆን አልቃጣችም:: በተለይ አሁን ከአማረ ጋር እንዴት እንደተለያየን ካወቅሁ በኋላና ያለ በደሉ በደለኛ አድርጌ መለያየቴን ስገነዘብ ፀፀቱ በፍጹም አላስቀምጥ አለኝ፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ እስካሁን አላግባብ ሳብጠለጥለው መኖሬን ሳስብና ከሁሉም በላይ ደግሞ ዶ/ር አድማሱ ያደረገውን ነገር ሁሉ እያወቅሁ፣ በምንም ተአምር ተመልሼ የእሱ ፍቅረኛ ሆኜ ልኖር እንደማልችል ይታየኛል፡፡ አርግጥ እሱ ለእኔ ካለው ፍቅር የተነሳ ያደረገው መሆኑን ስለማውቅ ጥፋቱን ሁሉ ይቅር ልለው እችላለሁ፣ ሆኖም እላይ
በጠቀስካቸው ምክንያቶች የተነሳ ዳግም የእሱ ፍቅረኛ ለመሆን ግን በምንም ሁኔታ አይቻለኝም:: የበደልኩትን ፍቅረኛዬን ፈልጌና እግሩ ላይ ወድቂ ይቅርታ ለመጠየቅ ወደ አንቺ እየመጣሁ ነው:: ቢያንስ ዳግም ባያፈቅረኝ እንኳ ይቅር ካለኝ ይበቃኛል" ይላል፡፡ ይህንን ደብዳቤ እንዳነበብኩ ራሴን መቆጣጠር ተሳነኝ፡ ከጽሑፉ ምሬት የተነሳ ሳልወድ በግድ ደጋግሜ አነበብኩት፤ በቃሌም አጠናሁት፡፡ ይህን በሕልሜም በውኔም ይሆናል ብዬ ያልጠበኩትን ነገር በራሷ የእጅ ጽሑፍ ሳነብ ውስጤ እሳት የተለኮሰበት ያህል ነደደ፡፡ ግን መጨከን አልቻልኩም፡፡ በዚሁ የተነሳ ጥላኝ ለመሄድ በተነሳችበት ዕለት ጨክኜ ላሰናብታት አልቻልኩም፡፡ ጽኑ ፍቅሬን እየገለጽኩላትና የወደፊቱን አስደሳች የሚሆን ሕይወታችንን በልዩ ልዩ መልክ እያብራራሁላት እንድትቀር ለመንኳት፡፡ እሷ ግን እምነቴንና ተስፋዬንም በእሷ ላይ ማሳደሬን በተደጋጋሚ ነግሬያት ሳለ ታደርገዋለች ብዬ በሙሉ ልቤ ሳላምን ጥላኝ ሄደች፡፡ ይህንን ሁሉ ውለታና ለእሷ ያለኝን ፍቅር ከምንም ሳትቆጥር ጥላኝ ወደ እዚህ እርኩስ ለመሄድ ወሰነች:: ለመንኳት፣ እግሯ ላይ ተንበርክኬ ቅሪ እያልኩ እያለቀስኩ ተማፀንኳት፣ ከእሷ ወዲያ ሕይወት ለእኔ ትርጉም እንደሌለው እና በእኔ ላይ በምትፈፅመው ነገር የኋላ ኋላ ከምትፀፀት ብትቀር እንደሚሻል ደጋግሜ ነገርኳት፡፡ አንጀት ካላት በማለት እንድትራራልኝ ጣርኩ፡፡ ለእሷ ግን ይህ ሁሉ መማፀን ምንም ዋጋ አልነበረውም:: እነዚህ ሁለት ደብዳቤዎች በእኔ መጻፋቸውን በማወቋ እጅግ አድርጋ ጠላቺኝ:: አፍ አውጥታ ለምን ይህንን እንዳደረኩ ግን ልትጠይቀኝ አልፈለገችም፡፡ ነገር ግን ይህ ድርጊቴም ቢሆን በእኔ ላይ እንዲህ የከፋ ጥላቻን ሊያስከትል የሚችል መሆን አልነበረበትም:: ምንም
እንኳን ድርጊቴ ጥሩ ባይሆንም ለእሷ ካለኝ ፍቅር የተነሳ እሷን ላለማጣትና ያንን የመሰለ ችሎታ ያላት ወጣት በአልባሌ ፍቅር ተተብትባ እንዳትቀር ያደረኩት መሆኑን ስለምታውቅ ይህንን ያህል የሚያስጨክን ነገር አልነበረም፡፡ እሷ ግን በተቃራኒው ልክ ትልቅ ወንጀል እንደፈፀምኩባት አድርጋ ሸሸችኝ፤ ጥላኝም ሄደች። በነጋታው ቤቱ ወና ሆነብኝ፡፡ ገና ከመሄዷ ብቸኝነት አስጨነቀኝ፡፡ ሌላ አማራጭ አልነበረኝምና ወደ እሷ መሄድ እንዳለብኝ ወሰንኩ፡፡ ግን ስሄድ በውስጤ ሁለት አማራጮችን ይዤ ነበር፡፡ ልመናዬን ሰምታ ከተመለሰች፤ ያፈጸመችብኝን በደል ሁሉ ረስቼ አብሬ ለመኖር፣ ይህ የማይሳከ ከሆነ ግን ተበቅዬ ለመምጣት፡፡ የምጠብቀው ካልተሳካም በማለት ለሁለተኛ አሰከፊ አማራጭ ተዘጋጅቼና ስልት አዘጋጅቼ እሷን ፍለጋዬን ጀመርኩ፡፡ በመጀመሪያ ድሬደዋ ካገኘኋት ብዬ ስፈልጋት አመሸሁ፡፡ ያላሰስኩት ሆቴል አልነበረም፤ ላገኛት ግን አልቻልኩም፡፡ በኋላ ግን ኤልሳ አዲስ አበባ
የሚገኘው ደብረወርቅ የተባለ ሆቴል ውስጥ አልጋ እንደያዘችላት የነገረችኝ ትዝ አለኝ፡፡ በነጋታው የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጬ ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ገባሁ። እንደገባሁም ሆቴሉ ድረስ ሄጄ ስጠይቅ፣ አልጋ እንደተያዘላት ነገር ግን እስከዚያ ሰዓት ድረስ እንዳልመጣች አስተናጋጁ ነገረኝ፡፡ መሸት እስከሚል ከተማውን እየዞርኩ ስናፈስ ቆይቼ ስመጣ ከተሾመ ጋር ስታወራ አየሁዋት:: እሷ ባታየኝም እኔ ግን ጥግ ላይ ተቀምጬ ሁኔታቸውን ሁሉ መከታተል ጀመርኩ፡፡ ግን ያንን ሳይ አለመምጣቴን ተመኘሁ፡፡ በምንም ታምር እኔን በተሾመ ትለውጣለች ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ ያን ያህል ካልሄድኩ ብላ ድርቅ ስትል፣ ደብዳቤ ላይ ባነበብኩት መሰረት ያቺ ኤልሳ ከዚህ ከደደብ ከአማረ ጋር ልታስታርቃት ፈልጋ የቀጠረቻት መሰለኝ እንጂ ወደዚህ የመጣችው በምንም ታምር ተሾመን ለማግኘት ነው ብዬ አልጠረጠርኩም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ይህንን ሳይ እሱ የተባረረ ጊዜ እሳት ጎርሳና እሳት ለብሳ ቢሮዬ ድረስ በመምጣት ያባረርኩት እኔ መሆኔንና አለመሆኔን የጠየቀችኝ ትዝ አለኝ፡፡ ግን ለምን? በወደድኳት ምን በደልኳት? ምን መጥፎ ነገር አድርጌ ነው እንዲህ የጠላችኝ? ለምንስ እኔን እንደጣዖት የማመልካትን ትታ ይኸን ባገኛት ቁጥር የሚቀጠቅጣትን ሰው መረጥች? ከእርሷ ተለይቼ ለአንዲት ደቂቃ እንኳን መቆየት እንደማልችል እያወቀች ለምን ጥላኝ ለመሄድ ወስነች? ከእኔ ምን አጣች? ከእነ ተሾመና አማረ ያገኘችውና ከእኔ ግን ያጣችው ምን ነገር ኖሮ ነው ጀርባዋን የሰጠችኝ? ነው ወይስ መውደዴን እንደወንጀል ቆጠረችው? በማለት ተማረርኩ፡፡ ለእሷ መንሰፍሰፌ ወንድነቴን አሳንሶና እኔነቴን አዋርዶ ያሳየብኝ መሰለኝ፡፡ ከተሾመ ተሰናብታ አስተናጋጁን ቢራ ክፍሏ ድረስ ይዞላት እንዲመጣ አዝዛ ወደ ክፍሏ እንደገባች የተዘጋጀሁበትን ሁለት አማራጮቼን ይዜ አስተናጋጁ ተከትዬ ወደተከራየችው ክፍል አመራሁ፡፡ _ ለእሱ በሩን ስትከፍትም ወደ ውስጥ ገብቼ በሩን ከኋላዬ ዘጋሁ፡፡ ያልጠበቀችው ነገር ስለነበር ስታየኝ ደነገጠች፡፡ ግባ ውጣም ሳትለኝ አልጋዋ ላይ ወጥታ ቁጭ አለች፡፡ ትንሽ ቆየት ብላም ለምን እንደመጣሁና እንዴት እዚህ አልጋ እንደያዘች እንዳወቅሁ ጠየቀችኝ፡፡ ተስፋ ሳለቆርጥ፣ ከእሷ ተለይቼ መኖር እንዳልቻልኩና እሷ ስትሄድ ቤቱ ወና እንደሆነብኝ በመንገር፣ ለፈጸምኩት በደል ሁሉ ይቅርታ አድርጋ ወደ ቤታችን እንድትመለስ እያለቀስኩና ጉንጯን እየሳምኩ ለምንኳት፡፡ ሁሉንም ነገር እንዳልተፈጸመ _ አድርጋ የደሰታ ሕይወታችንን እንኳ ባይሆን የደስታ ህይወቴን እንድቀጥል ዕድል እንድትሰጠኝና ከዚህ በኋላም ምንም እሷን የሚያስከፋ መጥፎ ነገር እንደማላደርግ ቃል እየገባሁ እንድትመለስ ተማጸንኳት፡፡
እሷ ግን እዚህ የመጣችው አማረን ፍለጋ መሆኑንና ያለ በደሉ በደለኛ አድርጋ መለያየቷን ስታውቅ ፀፀቱ በፍጹም አላስቀምጥ ስላላት ይቅርታ ለመጠየቅ እንደመጣች በድፍረት ነገረችኝ:: በዚህ ሳታበቃ በፊቷ ላይ ምንም የርህራሄ ገጽታ ሳይታይባት፣ እኔ ያፈጸምኩትን በደል ሁሉ እያወቀች በምንም ተአምር ተመልሳ የእኔ ፍቅረኛ ሆና መኖር እንደማይቻላት በመግለጽ መራራውን ሐቅ ሳልወድ በግድ ጋተችኝ :: ከዚህ በኋላ ግን መወሰን ነበረብኝና ወሰንኩ፡፡ ጊዜ ሳላጠፋ ቀደም ያወጣሁትን የበቀል ስልት ተጠቅሜ የማይቀረውን ርምጃዬን ሲል ወሰድኩ፡፡ አልጋዋ ላይ አጋድሜ በትራስ አፈንኳት፤ አየር አሳጣኋት፡፡ ትራሱን ከላይዋ ላይ ለማላቀቅ ብትሞክርም አልቻለችም፡፡ ቀስ በቀስ መተንፈስ እያቃተኝ ሄደ:: በመጨረሻም ተደሰትኩ እንጂ አላዘንኩም፡፡ ለዘላለም አሸለበች፡፡" የምሰማው ነገር ሁሉ በውኔ ሳይሆን በህልሜ መሰለኝ:: እሱ በእኔ ላይ ለፈፀመው በደል ተጠያቂ ሆኖ እያለ አላግባብ ያደረሰብኝ በደልና እንግልት ምንም ሳይመስለው በችሎት መኻል ይህ ደደብ ብሎ ሲጠራኝ ስሰማ በጣም አዘንኩ፡፡ በመግደሉ አለመፀፀቱም እጅግ ደነቀኝ፡፡ እኔ እንዲያ የምሳሳላትን ፍቅሬን በጭካኔ ገድሎ እና ይህም አልበቃም ብሎት ዳግም ተነስታ ቢያገኛት እንኳን ከመግደል እንደማይመለስ ሲናገርና በመግደሉ በመፀፀት ፋንታ ሲኩራራ መስማት እጅግ የሚያስደነግጥ ነበር፡፡ የእናትና አባት ፍቅር ማጣቷ በህይወቷ ላይ ጥሎት ያለፈውን ጠባሳ እያወቀ፣ ይህንኑ እንደጥፋት ቆጥሮ ሲወነጅላት በመስማቴም አዘንኩ፡፡ ከዚህ አልፎ ተርፎ ይህንን ሁሉ ወንጀል ከፈጸመ በኋላ ወንጀሉን ደብቆ በሰላም ለመኖር ሲል ራሷን የገደለች ለማስመሰል በማሰብ ሬሳዋን ሰቅሎ የክፍሏ የበር ቁልፉን ከደጅ ቆልፎ መሄዱን ሲተርክ ስሰማ የጭካኔው ደረጃ ዘገነነኝ:: በተለይ እሱ በጻፈው የሐሰት ደብዳቤ የተነሳ ራሷን እሱ ቤት ውስጥ ለማጥፋት በወሰነችበት ዕለት እሱ በወንጀሉ እንዳይጉላላ በማሰብ እራሷን እንደገደለች በመጥቀስ የጻፈችውን ደብዳቤ እስከዚያ ሰዓት ድረስ አስቀምጦ በወቅቱ ራሱን ከወንጀል ነፃ ለማድረግ እንደተጠቀመበት ስሰማ፣ ጨካኝና አልማዝ እንዳለችው ራስ ወዳድ ነው ብዬ ደመደምኩ፡፡ ግን ቆየት እያልኩ ሁኔታውን ሳየው በውስጤ ይንተከተክ የነበረው ንዴት ጠፍቶ በቦታው ሐዘን ተተካ፡፡ ፍቅሬም ልክ አሁን ገና የሞተች ያህል ተሰምቶኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩላት:: ስሜቴ ተመሰቃቀለ፡፡ ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለእሱም አዘንኩለት፡፡ ያን የመሰለ ምሁር በእርግጥ ጤነኛ ቢሆን ኖሮ ይህንን ሁሉ ወንጀል ባለፈፀመ፣ ከፈፅመ በኋላ ከመፀፀት ይልቅ እንዲህ በመግደሉ ባልተኩራራ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ፀጥታ ሰፈነበት:: ዳኛውም ፈዘው ቀሩ። ጠበቃዬ ለብዙ ወራቶች የደከመበት ጉዳይ እንዲህ ተሳክቶለት በሚፈልገው መልኩ በአሸናፊነት ሲጠናቀቅ እያየና እየሰማ በመደሰት ፋንታ በሰማው ነገር የደነገጠ መሰለ። ዋና ተዋናዩ ዶ/ር አድማሱ ግን ድራማውን መተወን ጀመረ:: ጥሩ ገድል ፈፅሞ የመጣ አርበኛ እስኪመስል ድረስ እያንዳንዱን ያደረገውን ድርጊት አንድም ሳያስቀር ተርኮ ጨረሰ:: ዳኛው በእኔ ላይ ሊፈረድ የነበረውን ፍርድ በእሱ ላይ አጠናክረው ፈርደው፣ የእሱን ነፃነት ለእኔ አጎናጽፈው፣ ውሳኔያቸውን ወስነውና ጠረጴዛውን በመዶሻቸው ጠልዘው ችሎቱን ዘጉ፡፡ የመዶሻ አመታታቸውም ለየት ያለ ድምፅ ነበረው:: ጠረጴዛውን ሳይሆን ወንጀለኛውን የመቱ ያህል ሳይሰማቸው አልቀረም፡፡ ዛሬ ለመጨረሻ ጊዜ ከሳጥኑ ውስጥ ነፃ ሰው ሆኜ ወጣሁ፡፡ ወዳጆቼ ሁሉ በደስታ ስከሩ፡፡ የሚያውቁኝ ብቻ ሳይሆኑ ችሎቱን ሲከታተሉ የነበሩ ሰዎች ሁሉ በልዩ ፈገግታ "እንኳን ደስ አለህ" አሉኝ:: እኔ ግን የምናገረው ጠፍቶኝ እምባዬ እንደጎርፍ ይወርድ ነበር፡፡ ለእኔ አልማዝ የሞተችው ገና
የሚገኘው ደብረወርቅ የተባለ ሆቴል ውስጥ አልጋ እንደያዘችላት የነገረችኝ ትዝ አለኝ፡፡ በነጋታው የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጬ ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ገባሁ። እንደገባሁም ሆቴሉ ድረስ ሄጄ ስጠይቅ፣ አልጋ እንደተያዘላት ነገር ግን እስከዚያ ሰዓት ድረስ እንዳልመጣች አስተናጋጁ ነገረኝ፡፡ መሸት እስከሚል ከተማውን እየዞርኩ ስናፈስ ቆይቼ ስመጣ ከተሾመ ጋር ስታወራ አየሁዋት:: እሷ ባታየኝም እኔ ግን ጥግ ላይ ተቀምጬ ሁኔታቸውን ሁሉ መከታተል ጀመርኩ፡፡ ግን ያንን ሳይ አለመምጣቴን ተመኘሁ፡፡ በምንም ታምር እኔን በተሾመ ትለውጣለች ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ ያን ያህል ካልሄድኩ ብላ ድርቅ ስትል፣ ደብዳቤ ላይ ባነበብኩት መሰረት ያቺ ኤልሳ ከዚህ ከደደብ ከአማረ ጋር ልታስታርቃት ፈልጋ የቀጠረቻት መሰለኝ እንጂ ወደዚህ የመጣችው በምንም ታምር ተሾመን ለማግኘት ነው ብዬ አልጠረጠርኩም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ይህንን ሳይ እሱ የተባረረ ጊዜ እሳት ጎርሳና እሳት ለብሳ ቢሮዬ ድረስ በመምጣት ያባረርኩት እኔ መሆኔንና አለመሆኔን የጠየቀችኝ ትዝ አለኝ፡፡ ግን ለምን? በወደድኳት ምን በደልኳት? ምን መጥፎ ነገር አድርጌ ነው እንዲህ የጠላችኝ? ለምንስ እኔን እንደጣዖት የማመልካትን ትታ ይኸን ባገኛት ቁጥር የሚቀጠቅጣትን ሰው መረጥች? ከእርሷ ተለይቼ ለአንዲት ደቂቃ እንኳን መቆየት እንደማልችል እያወቀች ለምን ጥላኝ ለመሄድ ወስነች? ከእኔ ምን አጣች? ከእነ ተሾመና አማረ ያገኘችውና ከእኔ ግን ያጣችው ምን ነገር ኖሮ ነው ጀርባዋን የሰጠችኝ? ነው ወይስ መውደዴን እንደወንጀል ቆጠረችው? በማለት ተማረርኩ፡፡ ለእሷ መንሰፍሰፌ ወንድነቴን አሳንሶና እኔነቴን አዋርዶ ያሳየብኝ መሰለኝ፡፡ ከተሾመ ተሰናብታ አስተናጋጁን ቢራ ክፍሏ ድረስ ይዞላት እንዲመጣ አዝዛ ወደ ክፍሏ እንደገባች የተዘጋጀሁበትን ሁለት አማራጮቼን ይዜ አስተናጋጁ ተከትዬ ወደተከራየችው ክፍል አመራሁ፡፡ _ ለእሱ በሩን ስትከፍትም ወደ ውስጥ ገብቼ በሩን ከኋላዬ ዘጋሁ፡፡ ያልጠበቀችው ነገር ስለነበር ስታየኝ ደነገጠች፡፡ ግባ ውጣም ሳትለኝ አልጋዋ ላይ ወጥታ ቁጭ አለች፡፡ ትንሽ ቆየት ብላም ለምን እንደመጣሁና እንዴት እዚህ አልጋ እንደያዘች እንዳወቅሁ ጠየቀችኝ፡፡ ተስፋ ሳለቆርጥ፣ ከእሷ ተለይቼ መኖር እንዳልቻልኩና እሷ ስትሄድ ቤቱ ወና እንደሆነብኝ በመንገር፣ ለፈጸምኩት በደል ሁሉ ይቅርታ አድርጋ ወደ ቤታችን እንድትመለስ እያለቀስኩና ጉንጯን እየሳምኩ ለምንኳት፡፡ ሁሉንም ነገር እንዳልተፈጸመ _ አድርጋ የደሰታ ሕይወታችንን እንኳ ባይሆን የደስታ ህይወቴን እንድቀጥል ዕድል እንድትሰጠኝና ከዚህ በኋላም ምንም እሷን የሚያስከፋ መጥፎ ነገር እንደማላደርግ ቃል እየገባሁ እንድትመለስ ተማጸንኳት፡፡
እሷ ግን እዚህ የመጣችው አማረን ፍለጋ መሆኑንና ያለ በደሉ በደለኛ አድርጋ መለያየቷን ስታውቅ ፀፀቱ በፍጹም አላስቀምጥ ስላላት ይቅርታ ለመጠየቅ እንደመጣች በድፍረት ነገረችኝ:: በዚህ ሳታበቃ በፊቷ ላይ ምንም የርህራሄ ገጽታ ሳይታይባት፣ እኔ ያፈጸምኩትን በደል ሁሉ እያወቀች በምንም ተአምር ተመልሳ የእኔ ፍቅረኛ ሆና መኖር እንደማይቻላት በመግለጽ መራራውን ሐቅ ሳልወድ በግድ ጋተችኝ :: ከዚህ በኋላ ግን መወሰን ነበረብኝና ወሰንኩ፡፡ ጊዜ ሳላጠፋ ቀደም ያወጣሁትን የበቀል ስልት ተጠቅሜ የማይቀረውን ርምጃዬን ሲል ወሰድኩ፡፡ አልጋዋ ላይ አጋድሜ በትራስ አፈንኳት፤ አየር አሳጣኋት፡፡ ትራሱን ከላይዋ ላይ ለማላቀቅ ብትሞክርም አልቻለችም፡፡ ቀስ በቀስ መተንፈስ እያቃተኝ ሄደ:: በመጨረሻም ተደሰትኩ እንጂ አላዘንኩም፡፡ ለዘላለም አሸለበች፡፡" የምሰማው ነገር ሁሉ በውኔ ሳይሆን በህልሜ መሰለኝ:: እሱ በእኔ ላይ ለፈፀመው በደል ተጠያቂ ሆኖ እያለ አላግባብ ያደረሰብኝ በደልና እንግልት ምንም ሳይመስለው በችሎት መኻል ይህ ደደብ ብሎ ሲጠራኝ ስሰማ በጣም አዘንኩ፡፡ በመግደሉ አለመፀፀቱም እጅግ ደነቀኝ፡፡ እኔ እንዲያ የምሳሳላትን ፍቅሬን በጭካኔ ገድሎ እና ይህም አልበቃም ብሎት ዳግም ተነስታ ቢያገኛት እንኳን ከመግደል እንደማይመለስ ሲናገርና በመግደሉ በመፀፀት ፋንታ ሲኩራራ መስማት እጅግ የሚያስደነግጥ ነበር፡፡ የእናትና አባት ፍቅር ማጣቷ በህይወቷ ላይ ጥሎት ያለፈውን ጠባሳ እያወቀ፣ ይህንኑ እንደጥፋት ቆጥሮ ሲወነጅላት በመስማቴም አዘንኩ፡፡ ከዚህ አልፎ ተርፎ ይህንን ሁሉ ወንጀል ከፈጸመ በኋላ ወንጀሉን ደብቆ በሰላም ለመኖር ሲል ራሷን የገደለች ለማስመሰል በማሰብ ሬሳዋን ሰቅሎ የክፍሏ የበር ቁልፉን ከደጅ ቆልፎ መሄዱን ሲተርክ ስሰማ የጭካኔው ደረጃ ዘገነነኝ:: በተለይ እሱ በጻፈው የሐሰት ደብዳቤ የተነሳ ራሷን እሱ ቤት ውስጥ ለማጥፋት በወሰነችበት ዕለት እሱ በወንጀሉ እንዳይጉላላ በማሰብ እራሷን እንደገደለች በመጥቀስ የጻፈችውን ደብዳቤ እስከዚያ ሰዓት ድረስ አስቀምጦ በወቅቱ ራሱን ከወንጀል ነፃ ለማድረግ እንደተጠቀመበት ስሰማ፣ ጨካኝና አልማዝ እንዳለችው ራስ ወዳድ ነው ብዬ ደመደምኩ፡፡ ግን ቆየት እያልኩ ሁኔታውን ሳየው በውስጤ ይንተከተክ የነበረው ንዴት ጠፍቶ በቦታው ሐዘን ተተካ፡፡ ፍቅሬም ልክ አሁን ገና የሞተች ያህል ተሰምቶኝ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩላት:: ስሜቴ ተመሰቃቀለ፡፡ ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለእሱም አዘንኩለት፡፡ ያን የመሰለ ምሁር በእርግጥ ጤነኛ ቢሆን ኖሮ ይህንን ሁሉ ወንጀል ባለፈፀመ፣ ከፈፅመ በኋላ ከመፀፀት ይልቅ እንዲህ በመግደሉ ባልተኩራራ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ፀጥታ ሰፈነበት:: ዳኛውም ፈዘው ቀሩ። ጠበቃዬ ለብዙ ወራቶች የደከመበት ጉዳይ እንዲህ ተሳክቶለት በሚፈልገው መልኩ በአሸናፊነት ሲጠናቀቅ እያየና እየሰማ በመደሰት ፋንታ በሰማው ነገር የደነገጠ መሰለ። ዋና ተዋናዩ ዶ/ር አድማሱ ግን ድራማውን መተወን ጀመረ:: ጥሩ ገድል ፈፅሞ የመጣ አርበኛ እስኪመስል ድረስ እያንዳንዱን ያደረገውን ድርጊት አንድም ሳያስቀር ተርኮ ጨረሰ:: ዳኛው በእኔ ላይ ሊፈረድ የነበረውን ፍርድ በእሱ ላይ አጠናክረው ፈርደው፣ የእሱን ነፃነት ለእኔ አጎናጽፈው፣ ውሳኔያቸውን ወስነውና ጠረጴዛውን በመዶሻቸው ጠልዘው ችሎቱን ዘጉ፡፡ የመዶሻ አመታታቸውም ለየት ያለ ድምፅ ነበረው:: ጠረጴዛውን ሳይሆን ወንጀለኛውን የመቱ ያህል ሳይሰማቸው አልቀረም፡፡ ዛሬ ለመጨረሻ ጊዜ ከሳጥኑ ውስጥ ነፃ ሰው ሆኜ ወጣሁ፡፡ ወዳጆቼ ሁሉ በደስታ ስከሩ፡፡ የሚያውቁኝ ብቻ ሳይሆኑ ችሎቱን ሲከታተሉ የነበሩ ሰዎች ሁሉ በልዩ ፈገግታ "እንኳን ደስ አለህ" አሉኝ:: እኔ ግን የምናገረው ጠፍቶኝ እምባዬ እንደጎርፍ ይወርድ ነበር፡፡ ለእኔ አልማዝ የሞተችው ገና
አሁን ነው:: ከሁሉም በላይ ካለጥፋቷ ይህንን ሁሉ ዘመን እንደ ጥፋተኛ ቆጥሬያት፤ በጥላቻና በከሀዲነት ፈርጄያት መቆየቴ ውስጥ ውስጡን አንገበገበኝ:: እውነቱን ለማወቅ እንኳን አንድም ጥረት ሳላደርግ በመኖሬ በተዘዋዋሪም ቢሆን ለሞቷ ተጠያቂ ነበርኩና ነፃ ነህ ብባልም ውስጤ ግን ነፃ የመሆን ስሜት በጭራሽ አልነበረውም። ከችሎቱ እንደወጣን በተገኘው ድል እጅግ የረኩና የተደሰቱት ኤልሳና ጠበቃዬ በደስታ ሰክረው ተቃቅፈው ተሳሳሙ፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ እያለሁ በፖሊስ ታጅቤ ከችሎቱ እንደወጣሁ፣ አንድ ሰው ከኋላዬ ጠራኝ፡፡ በሀሰት የመሰከረብኝ የሆቴሉ አስተናጋጅ ነበር፡፡ ብልጭ አለብኝ፤ "አሁን ደግሞ ምን ቀረህና ነው ስሜን የምትጠራው?" ብዬ አምባረቅሁበት፡፡ እሱ ግን ትህትና በተሞላው ሁኔታ፤ "ይቅርታ ያድርጉልኝ ጌቶች፡፡ እስቲ ተመልክቱ! ሰውዬው ከእርስዎ ጋር በጣም ይመሳሰላል፡፡ በሀሰት ለመመስከር ብዬ ሳይሆን መልካችሁ ተመሳስሎብኝ ተሳስቼ ነው" አለኝ፡፡ ይህንን ስሰማ አልማዝ መመሳሰላችንን አስመልክቶ የምትነግረኝ ትዝ ስላለኝ ለማረጋገጥ ዶ/ር አድማሱን አሻግሬ ማየት ጀመርኩ፡፡ በእርግጥም እኔኑ ነበር የሚመስለው፡፡ ዶ/ር አድማሱ በእኔ ምትክ በእኔው ካቴና ታስሮ ወደ መኪና ሲገባ አዘንኩለት፡፡ በፍ/ቤቱ ውሳኔ መሠረት ነፃ ሆኜ የምለቀቀው ወህኒ ቤት ወርጄ የመለቀቂያ ወረቀት ከተቀበልኩ በኋላ በመሆኑ ወደ ወህኒ ቤት ከሚወርደው ከዶ/ር አድማሱ ጋር ማዶ ለማዶ ተቀምጠን ተጓዝን፡፡ በእሱ ፊት ላይ የጥላቻ
ገፅታ ቢታይበትም እኔ ግን በሀዘን ስሜት ተመለከትኩት:: የነበረኝ ጥላቻ ሁሉ የት እንደገባ ባላውቅም የድሮው የእኔን እየወደድኩ የተጠላሁ አድርጎ የማየት ስሜት በእሱ ላይ ተገልጾ በማየቴና ይህንን ወንጀል እንዲፈፅም እንደገፋፋው በመረዳቴ አዘንኩለት፡፡ እየወደዱ አለመወደድ፣ እያፈቀሩ አለመፈቀር ከባድ ነውና ቢያሳዝነኝ የሚደንቅ አልነበረም:: ግን በመግደሉ ከመፀፀት ፋንታ መደሰቱንና ዳግም ለበቀል ያለውን ስሜት ሳጤነው፤ እጁ በደም ታጥቦም ቢሆን የሚጠራ አለመሆኑን ሳስብ ደግሞ ጭካኔው ያንገፈግፈኛል:: ዶ/ር አድማሱ ዓይኑን ከእኔ ላይ ሳይነቅል ግንባሩን አጨማዶ በንዴትና በጥላቻ ዓይን ያየኛል:: ግን ለምን እንዲህ ጠላኝ? እኔ እኮ ተስፋ ቆርጬ እሷን ለእሱ ትቼ፣ ሐሳብ ብቻ ታቅፌ የኖርኩና ከሐሳቤ ጋር እየታገልኩ እብደት ጠርዝ ላይ ቆሜ የይስሙላ ሕይወት ከመኖር ውጪ እሱን ለመጉዳትም ሆነ አልማዝን ለመበቀል አንድም ያደረኩት ነገር አልነበረም፡፡ እንደ እኔ ግምት እሷ ለእኔ እንዲህ የፀና ፍቅር አላት ብዬ አስቤም ሆነ አልሜ ስለማላውቅ ይህንን ሁሉ ዓመታት ላገኛት ከመመኘት ይልቅ እንዳላገኛት ስሸሽ የነበርኩ ሰው በመሆኔ ለእሱ ምንም አስጊ አልነበርኩበትም፡፡ ታዲያ ይህ ሆኖ እያለ ለምን ይህንን ያህል ሊጠላኝ ቻለ? እያልኩ ባለቀለት ጉዳይ መጨነቅ ጀመርኩ፡፡ በሁለተኛው ቀን ለመፈታት ስሜ ሲጠራ ከጓደኞቼ የመለያያው ቀን መድረሱን ተረዳሁት:: ጓደኞቼ የእስር ቤት ወጉ ሆኖ ተለይቻቸው ስሄድ ቅር ቢላቸውም፣ በመፈታቴ ደግሞ ተደስተዋል፡፡ እኔም ለመጀመሪያ ጊዜ ልክ ከቤተሰቦቹ እንደሚለያይ ሰው ሆዴን ባር ባር አለው፡፡ እምባዬም መውረዱን ቀጠለ:: እርግጥ ለአለፉት አራት ዓመታት ገደማ ቀንና ሌሊት ሳልለያቸው በየቀኑ ለሀያ አራት ሰዓታት አብሬ እየበላሁና እየጠጣሁ ያሳለፈኩ በመሆኔ እንደቤተሰብ ባያቸው የሚደንቅ አልነበረም፡፡ ከእነዚህ ጎደኞቼ ጋር ያሳለፍኩት አራት ዓመት፣ ምናልባት ቀን ትምህርት ቤት እየተማርኩና ከጓደኞቼ ጋር እየተጫወትኩ ያሳለፍኳቸው ሰዓታት እንዲሁም ዩንቨርስቲ ስማርና በስራ ላይ ሆኜ ያሳለፍኳቸው ጊዜያት ተቀንሰውበት ከሚቀረው ከቤተሰቦቼ ጋር ካሳለፍኩት ዓመታት ጋር ቢነጻጸር፣ ቢያንስ አንድ ስድሰተኛውን ሊሆን ስለሚችል ባለቅስ የሚበዛብኝ አልነበረም፡፡ ከወህኒ ቤት የመለቀቂያ ወረቀቴ ተዘጋጅቶ እንደተሰጠኝ ከግቢው ወጣሁ፡፡ ከእስር መፈታቴ ቢያስደስተኝም ወዴት ነው የምሄደው እያልኩ መጨነቅ ጀመርኩ፡፡ ቤት እንደሆነ የለኝም:: ሕይወቴ በብቸኝነት የተሞላ ስለነበር ደፍሬ የምሄድበት ጓደኛም አልነበረኝም:: አልቤርጎም እንዳልይዝ
ገንዘብ የሚባል ነገር ካየሁ ሰነባብቼአለሁ:: ያለኝ አማራጭ የቀድሞ አከራዮቼ ጋ ሄጄ ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ እነሱ ጋ መጠለል ብቻ ነው እያልኩ እየተጨነቅሁ አግቢው ስወጣ፣ ኤልሳና ጠበቃዬ በር ላይ ሲጠብቁኝ አገኘኋቸው፡፡ በቀጥታ ወደ እነሱ በጥድፊያ በመሄድ በሁለቱም የጋራ እቅፍ ውስጥ ገብቼ አንደበት ሊገልጸው ከሚችል የፍቅር ስሜት በላይ በሆነ ሁኔታ ተሳሳምን፡፡ ተያይዘንም በኤልሳ መኪናም ወደ እሷ ቤት አመራን፡፡ ኤልሳ ጋር ለሶስት ዓመታት ያህል ሊረሳ የማይችል ሕይወት አብረን አሳልፈን ስለነበር የእሷ ውለታ ብዙም አልከበደኝም ነበር። ለእኔ እንቆቅልሽ የሆነብኝና የከበደኝ ነገር ቢኖር ያለምንም ክፍያ እንደዚህ የደከመው የእጮኛዋ የጠበቃዬ ውለታ ነበር። ግን በምንም ዓይነት ሁኔታ ውለታውን ለመመለስ የሚያስችል አቅም ስላልነበረኝ ላደርገው የምችለው ነገር አመሰግናለሁ ማለት ብቻ ስለነበር ከልብ በመነጨ ስሜት "አመሰግናለሁ" አልኩት፡፡ ለእኔ ያደረጉትን ነገር ሳይና ደስታቸውን ስመለከትና መሰረት በሌለውና ሁለቱም በማያውቁት ነገር እነርሱን መጠርጠሬን ሳስብ፣ ነፃ ወጥቼ እንኳን የወንጀለኝነት ስሜት እንዲሰማኝ አደረገኝ፡፡ ውስጤ በዚህ እንደተጎዳ በደስታና በፀፀት ስሜት እያለቀስኩ፤ “ግን ለምን? ለምን ለእኔ ምንም ለማልጠቅም ምስኪን እንዲህ መድከም አስፈለገህ?'' አልኩት፡፡ “እኔ ላንተ ብዬ ሳይሆን ፍትህ ተጓድላ እንዳትቀር በመፈለግ ያደረኩት ተግባር ነው:: ትላንትም ሆነ ዛሬ ካንተ በላይ የተደሰትኩት እኔ ነኝ፡፡ ደስታዬ አንተ በመፈታትህ ብቻ ሳይሆን ሐቅ ተዳፍና ባለመቅረቷና አሸናፊ ሆና ስትወጣ በማየቴ ነው:: በሠራሁትም ሥራ ገንዘብ አላግኝ እንጂ የጥሩ ተግባር ዝናና የመንፈስ እርካታ አግኝቼበታለሁ፡፡ ዝናና በራስ መተማመን ካለ ደግሞ ያለምንም ጥርጥር ገንዘብ ተከትሎ ይመጣል" አለኝ:: ቀጠል አድርጎም በመቀለድ መልክ፤ “ከዚህ በላይ ደግሞ ከኤልሳ ጋር በቅርቡ ስለምንጋባና ይህንን በድል ከተወጣሁ ጥሎሽ እንደማልጠየቅ ስለተነገረኝ በተዘዋዋሪም ቢሆን ክፍያ ተከፍሎኛል ማለት ይቻላልና አትጨነቅ” በማለት ከት ብሎ ሳቀ፡፡ እኔም ከልቤ ፈገግ አልኩ፡፡ ቀስ በቀስ የነፃውን ሰው ዓለም _ እየለመድኩት መጣሁ:: አለቆቼ ያላግባብና ያለጥፋቴ ባሳለፍኩት የእስር ዓመታት እጅግ በጣም ስላዘኑ ወደ ሥራ እንዲመልሱኝ ስጠይቃቸው ምንም ሳያንገራግሩ ወዲያው አስገቡኝ፡
ትንሽ ቆይቼም የራሴን ቤት ተከራይቼ ሠራተኛዬ ቀድሞ አከራዮቼ ዘንድ አስቀምጣ የሄደችውን መጻሕፍትና እነ ኤልሳ የሰጡኝን አንድ አልጋ፣ አንድ ወንበርና አንድ ጠረጴዛ ይዤ እንደ አዲስ ጎጆ ወጪ ኑሮዬን "ሀ" ብዬ ጀመርኩ:: ከዚህ ውጪ አለኝ የምለው አንድ ታሪካዊ ንብረት ቢኖር ከፖሊስ ጣቢያ ያመጣሁት ዲያሪ ነበር:: በአልማዝ ፋንታ የቀረኝ ነገር ቢኖር ይኼው የእሷ የእጅ ጽሑፏ ነው:: ለምን እንደሆነ ባይገባኝም ደግሜ ደጋግሜ አነበብኩት። ባነበብኩት ቁጥርም የማነበው የእሷን የእጅ ጽሑፍ ሳይሆን ቁጭ ብላ የምታወራኝ ያህል ሆኖ ይሰማኛል:: ታሪኩ በመደምደሙና ፍጻሜውም እንዲሁ የታወቀ በመሆኑ እንደበፊቱ ለማንበብ ባያጓጓኝም፣ ቀደም ብዬ ሳነበው በነበረ ጊዜ አልፈታ ያሉኝ እንቆቅልሾች እንዲህ በቀላሉ በእውነት ኃያልነት ሊፈቱ ይችሉ እንደነበር ሳስብና ለዚህ ሁሉ ጊዜ ይህንን ለመረዳት አለመቻሌን ሳስታውስ፤ ዶ/ር አድማሱ "ያንን ደደብ…" ብሎ
ገፅታ ቢታይበትም እኔ ግን በሀዘን ስሜት ተመለከትኩት:: የነበረኝ ጥላቻ ሁሉ የት እንደገባ ባላውቅም የድሮው የእኔን እየወደድኩ የተጠላሁ አድርጎ የማየት ስሜት በእሱ ላይ ተገልጾ በማየቴና ይህንን ወንጀል እንዲፈፅም እንደገፋፋው በመረዳቴ አዘንኩለት፡፡ እየወደዱ አለመወደድ፣ እያፈቀሩ አለመፈቀር ከባድ ነውና ቢያሳዝነኝ የሚደንቅ አልነበረም:: ግን በመግደሉ ከመፀፀት ፋንታ መደሰቱንና ዳግም ለበቀል ያለውን ስሜት ሳጤነው፤ እጁ በደም ታጥቦም ቢሆን የሚጠራ አለመሆኑን ሳስብ ደግሞ ጭካኔው ያንገፈግፈኛል:: ዶ/ር አድማሱ ዓይኑን ከእኔ ላይ ሳይነቅል ግንባሩን አጨማዶ በንዴትና በጥላቻ ዓይን ያየኛል:: ግን ለምን እንዲህ ጠላኝ? እኔ እኮ ተስፋ ቆርጬ እሷን ለእሱ ትቼ፣ ሐሳብ ብቻ ታቅፌ የኖርኩና ከሐሳቤ ጋር እየታገልኩ እብደት ጠርዝ ላይ ቆሜ የይስሙላ ሕይወት ከመኖር ውጪ እሱን ለመጉዳትም ሆነ አልማዝን ለመበቀል አንድም ያደረኩት ነገር አልነበረም፡፡ እንደ እኔ ግምት እሷ ለእኔ እንዲህ የፀና ፍቅር አላት ብዬ አስቤም ሆነ አልሜ ስለማላውቅ ይህንን ሁሉ ዓመታት ላገኛት ከመመኘት ይልቅ እንዳላገኛት ስሸሽ የነበርኩ ሰው በመሆኔ ለእሱ ምንም አስጊ አልነበርኩበትም፡፡ ታዲያ ይህ ሆኖ እያለ ለምን ይህንን ያህል ሊጠላኝ ቻለ? እያልኩ ባለቀለት ጉዳይ መጨነቅ ጀመርኩ፡፡ በሁለተኛው ቀን ለመፈታት ስሜ ሲጠራ ከጓደኞቼ የመለያያው ቀን መድረሱን ተረዳሁት:: ጓደኞቼ የእስር ቤት ወጉ ሆኖ ተለይቻቸው ስሄድ ቅር ቢላቸውም፣ በመፈታቴ ደግሞ ተደስተዋል፡፡ እኔም ለመጀመሪያ ጊዜ ልክ ከቤተሰቦቹ እንደሚለያይ ሰው ሆዴን ባር ባር አለው፡፡ እምባዬም መውረዱን ቀጠለ:: እርግጥ ለአለፉት አራት ዓመታት ገደማ ቀንና ሌሊት ሳልለያቸው በየቀኑ ለሀያ አራት ሰዓታት አብሬ እየበላሁና እየጠጣሁ ያሳለፈኩ በመሆኔ እንደቤተሰብ ባያቸው የሚደንቅ አልነበረም፡፡ ከእነዚህ ጎደኞቼ ጋር ያሳለፍኩት አራት ዓመት፣ ምናልባት ቀን ትምህርት ቤት እየተማርኩና ከጓደኞቼ ጋር እየተጫወትኩ ያሳለፍኳቸው ሰዓታት እንዲሁም ዩንቨርስቲ ስማርና በስራ ላይ ሆኜ ያሳለፍኳቸው ጊዜያት ተቀንሰውበት ከሚቀረው ከቤተሰቦቼ ጋር ካሳለፍኩት ዓመታት ጋር ቢነጻጸር፣ ቢያንስ አንድ ስድሰተኛውን ሊሆን ስለሚችል ባለቅስ የሚበዛብኝ አልነበረም፡፡ ከወህኒ ቤት የመለቀቂያ ወረቀቴ ተዘጋጅቶ እንደተሰጠኝ ከግቢው ወጣሁ፡፡ ከእስር መፈታቴ ቢያስደስተኝም ወዴት ነው የምሄደው እያልኩ መጨነቅ ጀመርኩ፡፡ ቤት እንደሆነ የለኝም:: ሕይወቴ በብቸኝነት የተሞላ ስለነበር ደፍሬ የምሄድበት ጓደኛም አልነበረኝም:: አልቤርጎም እንዳልይዝ
ገንዘብ የሚባል ነገር ካየሁ ሰነባብቼአለሁ:: ያለኝ አማራጭ የቀድሞ አከራዮቼ ጋ ሄጄ ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ እነሱ ጋ መጠለል ብቻ ነው እያልኩ እየተጨነቅሁ አግቢው ስወጣ፣ ኤልሳና ጠበቃዬ በር ላይ ሲጠብቁኝ አገኘኋቸው፡፡ በቀጥታ ወደ እነሱ በጥድፊያ በመሄድ በሁለቱም የጋራ እቅፍ ውስጥ ገብቼ አንደበት ሊገልጸው ከሚችል የፍቅር ስሜት በላይ በሆነ ሁኔታ ተሳሳምን፡፡ ተያይዘንም በኤልሳ መኪናም ወደ እሷ ቤት አመራን፡፡ ኤልሳ ጋር ለሶስት ዓመታት ያህል ሊረሳ የማይችል ሕይወት አብረን አሳልፈን ስለነበር የእሷ ውለታ ብዙም አልከበደኝም ነበር። ለእኔ እንቆቅልሽ የሆነብኝና የከበደኝ ነገር ቢኖር ያለምንም ክፍያ እንደዚህ የደከመው የእጮኛዋ የጠበቃዬ ውለታ ነበር። ግን በምንም ዓይነት ሁኔታ ውለታውን ለመመለስ የሚያስችል አቅም ስላልነበረኝ ላደርገው የምችለው ነገር አመሰግናለሁ ማለት ብቻ ስለነበር ከልብ በመነጨ ስሜት "አመሰግናለሁ" አልኩት፡፡ ለእኔ ያደረጉትን ነገር ሳይና ደስታቸውን ስመለከትና መሰረት በሌለውና ሁለቱም በማያውቁት ነገር እነርሱን መጠርጠሬን ሳስብ፣ ነፃ ወጥቼ እንኳን የወንጀለኝነት ስሜት እንዲሰማኝ አደረገኝ፡፡ ውስጤ በዚህ እንደተጎዳ በደስታና በፀፀት ስሜት እያለቀስኩ፤ “ግን ለምን? ለምን ለእኔ ምንም ለማልጠቅም ምስኪን እንዲህ መድከም አስፈለገህ?'' አልኩት፡፡ “እኔ ላንተ ብዬ ሳይሆን ፍትህ ተጓድላ እንዳትቀር በመፈለግ ያደረኩት ተግባር ነው:: ትላንትም ሆነ ዛሬ ካንተ በላይ የተደሰትኩት እኔ ነኝ፡፡ ደስታዬ አንተ በመፈታትህ ብቻ ሳይሆን ሐቅ ተዳፍና ባለመቅረቷና አሸናፊ ሆና ስትወጣ በማየቴ ነው:: በሠራሁትም ሥራ ገንዘብ አላግኝ እንጂ የጥሩ ተግባር ዝናና የመንፈስ እርካታ አግኝቼበታለሁ፡፡ ዝናና በራስ መተማመን ካለ ደግሞ ያለምንም ጥርጥር ገንዘብ ተከትሎ ይመጣል" አለኝ:: ቀጠል አድርጎም በመቀለድ መልክ፤ “ከዚህ በላይ ደግሞ ከኤልሳ ጋር በቅርቡ ስለምንጋባና ይህንን በድል ከተወጣሁ ጥሎሽ እንደማልጠየቅ ስለተነገረኝ በተዘዋዋሪም ቢሆን ክፍያ ተከፍሎኛል ማለት ይቻላልና አትጨነቅ” በማለት ከት ብሎ ሳቀ፡፡ እኔም ከልቤ ፈገግ አልኩ፡፡ ቀስ በቀስ የነፃውን ሰው ዓለም _ እየለመድኩት መጣሁ:: አለቆቼ ያላግባብና ያለጥፋቴ ባሳለፍኩት የእስር ዓመታት እጅግ በጣም ስላዘኑ ወደ ሥራ እንዲመልሱኝ ስጠይቃቸው ምንም ሳያንገራግሩ ወዲያው አስገቡኝ፡
ትንሽ ቆይቼም የራሴን ቤት ተከራይቼ ሠራተኛዬ ቀድሞ አከራዮቼ ዘንድ አስቀምጣ የሄደችውን መጻሕፍትና እነ ኤልሳ የሰጡኝን አንድ አልጋ፣ አንድ ወንበርና አንድ ጠረጴዛ ይዤ እንደ አዲስ ጎጆ ወጪ ኑሮዬን "ሀ" ብዬ ጀመርኩ:: ከዚህ ውጪ አለኝ የምለው አንድ ታሪካዊ ንብረት ቢኖር ከፖሊስ ጣቢያ ያመጣሁት ዲያሪ ነበር:: በአልማዝ ፋንታ የቀረኝ ነገር ቢኖር ይኼው የእሷ የእጅ ጽሑፏ ነው:: ለምን እንደሆነ ባይገባኝም ደግሜ ደጋግሜ አነበብኩት። ባነበብኩት ቁጥርም የማነበው የእሷን የእጅ ጽሑፍ ሳይሆን ቁጭ ብላ የምታወራኝ ያህል ሆኖ ይሰማኛል:: ታሪኩ በመደምደሙና ፍጻሜውም እንዲሁ የታወቀ በመሆኑ እንደበፊቱ ለማንበብ ባያጓጓኝም፣ ቀደም ብዬ ሳነበው በነበረ ጊዜ አልፈታ ያሉኝ እንቆቅልሾች እንዲህ በቀላሉ በእውነት ኃያልነት ሊፈቱ ይችሉ እንደነበር ሳስብና ለዚህ ሁሉ ጊዜ ይህንን ለመረዳት አለመቻሌን ሳስታውስ፤ ዶ/ር አድማሱ "ያንን ደደብ…" ብሎ
የተናገረው ምናልባት ትንሽም ቢሆን እውነትነት ሳይኖረው አይቀርም ብዬ ማሰቤ ግን አልቀረም፡፡ ያም ሆነ ይህ! ሁሉ ነገር ባልጠበቁትና ባልገመትኩት መንገድ ተጠናቀቀ፡፡ እኔ እንደተመኘሁት ሳይሆን ሕይወት በፈለገችበት አቅጣጫና መንገድ ያለማንም ከልካይ እንዳሻት ተጓዘች፡፡ የእኔ የመከራ ሕይወትም ያለፈው ውስብስብ ታሪክን ሰንቆ ሕይወት ወደ መራችው ለመሄድ ኋላ ኋላ ድክ ድክ እያለ መከተሉን ቀጠለ፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ፣ ቅደም ተከተሉ እና በግብግቡ ውስጥ የነበሩት አያሌ ድርጊቶችና ፈተናዎች አንድም ሳይዛቡ፣ እነሆ የአልማዝ ሕያው ዲያሪ እስከ ኅልፈተ ሕይወቴ ድረስ በሕሊናዬ ውስጥ ተቀርጾ ይኖራል፡፡ በእጄ በያዝኩት ዲያሪ ውስጥ ደግሞ የአልማዝ ፍቅርና ምኞት፣ ተስፋና ትዝታ፣ ዓላማ እና ግብ እየተዋሀደበት የእኔና የእሷ ያልተጻፈ የሕይወት ጥምር ዲያሪ ፍሰት ይቀጥላል...
ተፈፀመ።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ተፈፀመ።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡
‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት
‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››
‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡
አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ
‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡
‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››
‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››
‹‹ድንግልናሽን?››
‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››
‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…
‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡
‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››
‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››
‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››
‹‹ማለት?››
‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡
‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››
‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡
‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡
‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››
‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››
‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››
‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››
‹‹ምን ያስፈራሀል?››
‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››
‹‹እንዴት …?››
‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››
‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››
‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››
‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››
‹‹ማለት?፡፡››
‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡
‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡
‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡
‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡
‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››
‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››
‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡
‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡
አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››
ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡
በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡ ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡
በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡
‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት
‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››
‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡
አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ
‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡
‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››
‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››
‹‹ድንግልናሽን?››
‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››
‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…
‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡
‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››
‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››
‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››
‹‹ማለት?››
‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡
‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››
‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡
‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡
‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››
‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››
‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››
‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››
‹‹ምን ያስፈራሀል?››
‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››
‹‹እንዴት …?››
‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››
‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››
‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››
‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››
‹‹ማለት?፡፡››
‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡
‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡
‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡
‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡
‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››
‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››
‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡
‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡
አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››
ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡
በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡ ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡
በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
ዘሚካኤል ውስጧ ሊፈነዳ የነበረውን ፊውዝ አብርቷላት ነበር። እሷን መንካት እና መሳም እንዲቀጥል ፈለገች፣ መፍራት ሰልችቷታል። እያንዳንዷ ሴት ልትመኘው የሚገባትን አይነት ግንኙነት ውስጥ ነች… የራሷን ስሜት መካድ ሰልችቶታል…እንዲህ አይነት ሁኔታ ከዚህ በፊት ፈልጋ አታውቅም። ከልጅነት ፍቅረኛዋ ጋር እንኳን ፈልጋ ሳይሆን በአንድ ክፉ ቀን ስህተት የፈፀመችው ነው። አሁን ግን ከልቧ የሚደረገውን ሁሉ ለማድረግ ተመኘች። ከስድስት ዓመት በፊት የሆነውን ነገር አስታወሰች..ነገሮች በዛ መልኩ እንዳይሄዱና ተመሳሳይ አይነት ስብራት እንዲያጋጥማት አትፈልግም…ይሄንን እዚህ አሁን ያለችበትን የስሜት ቃጠሎ ውስጥም ሆና ልትዘነጋው አትችልም፡፡
‹‹እስቲ ስለመሄድ ቢያንስ ለጊዜው እርሺው›› አላት
እጆቾን በደረታቸው መካከል አስገባችና በቀስታ ገፋችውና‹‹እሺ..ግን ይሄ ለዛሬ ብቻ የሚሆንና መቼም የማይደገም ነው›› አለችው፡፡
በአልተለመደ ንግግሯ ሳቀ
‹‹ምን ያስቅሀል?››አለችው፡፡
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 መግባት አለበት ይሄ ድርሰት እስከሚያልቅ
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹እስቲ ስለመሄድ ቢያንስ ለጊዜው እርሺው›› አላት
እጆቾን በደረታቸው መካከል አስገባችና በቀስታ ገፋችውና‹‹እሺ..ግን ይሄ ለዛሬ ብቻ የሚሆንና መቼም የማይደገም ነው›› አለችው፡፡
በአልተለመደ ንግግሯ ሳቀ
‹‹ምን ያስቅሀል?››አለችው፡፡
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 መግባት አለበት ይሄ ድርሰት እስከሚያልቅ
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ…ምንድነው ያሳቀህ?››
‹‹በጣም ነው እንጂ የሚያስቀው…ማንም ሴት እንዲህ አይነት መደራደሪያ አቅርባልኝ አታውቅም››
‹‹እኔ እኔ ነኝ ..ስለሌሎች ሴቶች አላውቅም፡፡››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ አለሽ እንዴ?››በአእምሮ ሲያብሰለስል የነበረው ጥያቄ ጠየቃት፡፡
አፈጠጠችበት..ደነገጠም ..ግራ ተጋባም
‹‹እንዴ …ምን መጥፎ ነገር ተናገርኩ?››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ ቢኖረኝ እዚህ ከአንተ ጋር ምን ያንዘላዝለኛል?፡፡››
ወደራሱ ጎተተና ከንፈሯ ላይ ተጠጣበቀባት…ተቃውሞ አላሰማችም..እንደውም ቀስ ብላ እጆቾን አነሳችና በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመች…አልጋውን ለቃ እየተንሳፈፈች እንደሆነ አይነት ምትሀታዊ አይነት ስሜት እየተሳማት ነው፡፡
የልቧን ምት ፍጥነት መቆጣጠር ስላልቻለችና መተንፈስም ስለከበዳት እየፈለገች ግን ከንፈሯን ከከንፈሩ አላቀቀችና
፣‹‹የሚጠጣ ነገር ይኖራል?››
ስትል ጠየቀችው፡፡መጠጥ የጠየቀችው በወሲብ ወቅት ድፍረት ይሰጣል ሲባል ስለሰማች ነው፡፡
‹‹አዎ አለ፡፡››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ… ለእሱም ለእሷም መጠጥ ይዞ መጣና ጠረጴዛውን ወደ አልጋው አስጠግቶ ከጎኗ ተመልሶ ቁጭ አለ፡፡
‹‹ምነው ይሄን ያህል አስፈራለሁ እንዴ?››
‹‹አይ በፍፅም…..ግን ››ንግግሯን አቋረጠችና ስልኳን ካስቀመጠችበት ኮመዲኖ ተንጠራርታ አነሳችና..ከፍታ ሰጠችው፡፡
‹‹ምንድነው?››
ተቀበላትና ተመለከተ..ውብ ቆንጅዬ የምታምር ልጅ ፎቶ ይታያል፡፡ግራ ገባውና ቀና ብሎ በትኩረት አያት‹‹ልጄ ነች…ስድስት አመቷ ነው፡፡››
‹‹ምን …?››ከተቀመጠበት ተነሳ…አፍጥጦ ፎቶውን መመለክት ጀመረ፡፡
በሁኔታው ተበሳጨች….‹‹… ዝም ብዬ እንድታውቀው ስለፈለኩ ነው እንጂ ይሄን ያህል ምን ያስደነግጥሀል…?አታገባኝ ወይ አትወሽመኝ ..አንድ ልጅ ኖረኝ አምስት ምን አጨናነቀህ…?››
በቆመበት አፍጥጦ በዝምታ ያያት ጀመር፡፡ያ ደግሞ የበለጠ ንዴቷን እንዲጨምር አደረገ…‹‹እንደውም ሁሉ ነገር እዚህ ላይ ያብቃ ወደቤቴ ልሂድ››ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ተንደርድሮ መጥቶ ትከሻዋን ይዞ አስቀመጣትና ግንባሯን ሳማት፡፡
‹‹በጣም ነጭናጫ ሴት መሆንሽን ታውቂያለሽ?››
‹‹እንኳን››
‹‹እኔ ይህቺን የመሰለች ልጅ ስላለሽ ቀናሁብሽ እንጂ አልተበሳጨሁበሽም…በጣም እኮ ነው የምታምረው…..ደግሞ በስንት አመትሽ ብትወልጂያት ነው እንዲህ ያደገችው?››
‹‹በ17››
‹‹እና የት ነው ያለችው ..ከአንቺ ጋር ወይስ አባቷ ጋር?››
‹‹አባቷ መፀናሷን እንዳወቀ ነው ሸሽቶ ውትድርና ተቀጥሮ የጠፋው..እስከአሁን ይኑር ይሙት አላውቅም…እሷ ከእኔ ጋር ነው ያለችው፡፡››
‹‹እና አሁን እቤት ነው ያለቻ ?ብንሄድ እናገኛታለን?››
በመገረም አፍጥጣ ተመለከተችው‹‹የእውነት አሁን እንሂድ ብልህ ትሄዳለህ?››
‹‹አዎ..››ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ …‹‹ሰዓቱ ገና ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ከ10 ነው …ተነሽ እንደውም….የሆነ ነገር ገዝተንላት እንሂድ እና እናስደስታት፡፡››
እሱ ጃኬቱን ሲለብስ እሷ ከተቀመጠችበት ሳትንቀሳቀስ በገረሜታ አፏን ከፈተችና በፍዘት ታየው ነበር፡፡
‹‹አልሰማሺኝም እንዴ? ተነሽ እንሂድ››
‹‹ልጅ ማትወድ መስሎኝ ነበር››
በተራው ደነገጠ…‹‹እንዴ ምን ማለት ነው…?እንዴት እንደዛ ልታስቢ ቻልሽ?››
‹‹ቅድም የወንድምህን ልጅ ወደአንተ ይዤ መጥቼ ሳስተዋውቅህ..ከእቅፌ ወስደህ አቅፈህ የምትስመው መስሎኝ ነበር…ግን እንደዛ አላደረክም..ጉንጩን አንኳን አልሳምክም››
ወደእሷ መጣና ከጎኗ ተቀመጠ‹‹ያን ያህል ስትታዘቢኝ ነበር ማለት ነው…?ላቅፈውና ልስመው በጣም ነበር የፈለኩት….አጎትህ ነኝ ብዬ እሽኮኮ በማድረግ ከሆቴሉ ይዤው ወጥቼ ላዝናናው ሁሉ ፈልጌ ነበር..ግን አልቻልኩም…ምክንያቱም የወንድሜ ልጅ ነው ፤ስለወንድሜ ሳስብ ደግሞ በደረቷ ቢላዋ ተሰክቶባት ወለል ላይ የተዘረጋች እናቴና በገመድ የተንጠለጠለች እህቴ ነች ወደአእምሮዬ የምትመጣው…በዛን ወቅት አሰብ የነበረው ስለእነሱ ነበር …እንባዬ እንዳያመልጠኝና በሰርግ እድምተኞች ፊት እንዳልዋረድ እየጣርኩ ነበር››እንባው ከአይኖቹ እየተዘረገፈ መውረድ ጀመረ፡፡ ደነገጠችና ከተቀመጠችበት ተነሳች በእጇቾ እንባውን እበሰችና ግንበሩን ጉንጮቹን እያገላበጠች እየሰማች‹‹ይቅርታ…በጣም ይቅርታ…እኔ እንዲህ አይነት ቀሽም ሴት ነኝ…ሶሪ ወንዶችን ሰላማላምን ሁሉን ነገር ነው የምጠራጠረው…ከልጄ አባት ውጭ ሌላ ወንድ አላውቅም…ከአንተ ጋር በእንደዚህ አይነት መጠን መቀራረብና በአንድ ክፍል ውስጥ መሆን በጣም ቢያስደስተኝም በዛው መጠን አስፈርቶኛል….ለዛ ነው ያልሆነ ነገር የምቀባጥረው፡፡››
‹‹ችግር የለውም… ተረድቼሻለው››
‹‹በቃ በፈጣሪ ያልኩህን ሁሉ እርሳው…››ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት..በጠንካራ እጆቹን በቀጭን ወገቧ ዙሪያ ጠመጠመና ከሰውነት ጋር ለጥፎ ትንፋሽ እስኪያጥራት መጠጣት…..ከዛ ለቀቃትና..‹‹በይ አታረሳሺኝ ተነሽ እንሂድ››
‹‹በእውነት ቢሆንና ብታይህ በጣም ነበር የምትደሰተው…ሙዚቀዎችህን በጣም ነው የምትወዳቸው…ግን አሁን የለችም››
‹‹የለችም ማለት?››
‹‹አሁን ክረምት አይደል..ትምህርት ስለተዘጋ አያቶቾ ወስደዋታል….የሚቀጥለውን አንድ ወር እነሱ ጋር ነው የምታሳለፈው….››
‹‹እ ያሳዝናል…እንግዲህ ምን ማድረግ ይቻላል ስትመለስ ታስተዋውቂኛለሽ››
‹ስትመለስ?››አለችና ሳቀች፡፡
‹‹ምን ያስቅሻል?››
‹‹የዛሬ ወር እኮ ነው ያልኩህ…››
‹‹ምነው የዛሬ ወር የለሁም እንዴ..?አለሁ እኮ ፤ማለቴ በፍቅርሽ አሟሙተሸ ካላጠፋሺኝ አለው..››
‹‹ይሁን እስኪ…..ለማንኛውም አስገርመሀኛል››አለችና የመጠጡን ብርጭቆ አነስታ ተጎነጨች፡፡
‹‹እድሉን እስከሰጠሺን ድረስ ገና ብዙ አሰግርምሻለው፡፡››
ከዛ ቀልል ያለ ወሬ እያወሩ ከመጠጡ መጎንጨታቸውን ቀጠሉ….
‹‹ይሞቃል አይደል?››አለችው የእውነትም በጣም እየሞቃት ነው…ያላወቀችው የሙቀቱ ምንጭ ከምትጠጣው መጠጥ ይመንጭ ወይም ከጎኗ ካለው ሸበላ ወይም ከአየር ፀባዩ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡
‹‹እኔም ሞቋኛል …››አለና ጃኬቱን አወለቀ፡፡
‹‹እኔስ ቀሚሴን ላውልቅ?››አለችውና ሳቀች፡፡
‹‹ይቻላል..ቆይ እንደውም..›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ወደሻንጣው በመሄድ ከፈተው፡፡ምን ሊያደርግ ነው ብላ በትኩረት እየተከታተለችው ነው፡፡
ስስ ቁምጣ እና ቲሸርት አወጣና…እንቺ ቀሚሱን አውልቂና ይሄን ልበሺ አለና ለራሱ ሌላ ቢጃማ በማውጠት ሱሪውን ለማውለቅ ቀበቷውን መፍታት ጀመረ፡፡
‹‹ምን እያደረክ ነው?››
‹‹ሱሬዬን ልቀይር ነዋ….››
ሱሪውን ወደታች አወለቀ..ከዛ ከላይ የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ..በነጭ ፓካውትና በሰማያዊ ፓንት ብቻ በሁለት ሜትር ርቀት ቆሞ ስትመለከት ሰውነቷን ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ነገር አንዘረዘራት፡፡በልብስ ከሚታየው ይልቅ እርቃኑን ያምራል…ደግሞ ከፊል ሰውነቱ በተለያዩ ማራኪ ንቅሳቶች የተዥጎረጎረ ነው፡፡
‹‹ምነው ፈዘዝሽ?››ብሎ አሳፈራት፡፡
‹‹ምን ፈዛለው…እንደ ሸራ በስእል ተዥጎርጉረህ የለ እንዴ?››
የሚቀይረውን ቢጃማ ሱሪ አነሳና በእጁ እንደያዘ‹‹ያምራል አይደል…?እስኪ በደንብ ተመልከቺው ››አለና ይበልጥ ወደእሷ ተጠጋና ስሯ ቆመ፡፡
ዝም አለች ..ጎትቶ አስነሳት‹‹እንዴ ምን እያደረክ ነው?››
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ…ምንድነው ያሳቀህ?››
‹‹በጣም ነው እንጂ የሚያስቀው…ማንም ሴት እንዲህ አይነት መደራደሪያ አቅርባልኝ አታውቅም››
‹‹እኔ እኔ ነኝ ..ስለሌሎች ሴቶች አላውቅም፡፡››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ አለሽ እንዴ?››በአእምሮ ሲያብሰለስል የነበረው ጥያቄ ጠየቃት፡፡
አፈጠጠችበት..ደነገጠም ..ግራ ተጋባም
‹‹እንዴ …ምን መጥፎ ነገር ተናገርኩ?››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ ቢኖረኝ እዚህ ከአንተ ጋር ምን ያንዘላዝለኛል?፡፡››
ወደራሱ ጎተተና ከንፈሯ ላይ ተጠጣበቀባት…ተቃውሞ አላሰማችም..እንደውም ቀስ ብላ እጆቾን አነሳችና በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመች…አልጋውን ለቃ እየተንሳፈፈች እንደሆነ አይነት ምትሀታዊ አይነት ስሜት እየተሳማት ነው፡፡
የልቧን ምት ፍጥነት መቆጣጠር ስላልቻለችና መተንፈስም ስለከበዳት እየፈለገች ግን ከንፈሯን ከከንፈሩ አላቀቀችና
፣‹‹የሚጠጣ ነገር ይኖራል?››
ስትል ጠየቀችው፡፡መጠጥ የጠየቀችው በወሲብ ወቅት ድፍረት ይሰጣል ሲባል ስለሰማች ነው፡፡
‹‹አዎ አለ፡፡››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ… ለእሱም ለእሷም መጠጥ ይዞ መጣና ጠረጴዛውን ወደ አልጋው አስጠግቶ ከጎኗ ተመልሶ ቁጭ አለ፡፡
‹‹ምነው ይሄን ያህል አስፈራለሁ እንዴ?››
‹‹አይ በፍፅም…..ግን ››ንግግሯን አቋረጠችና ስልኳን ካስቀመጠችበት ኮመዲኖ ተንጠራርታ አነሳችና..ከፍታ ሰጠችው፡፡
‹‹ምንድነው?››
ተቀበላትና ተመለከተ..ውብ ቆንጅዬ የምታምር ልጅ ፎቶ ይታያል፡፡ግራ ገባውና ቀና ብሎ በትኩረት አያት‹‹ልጄ ነች…ስድስት አመቷ ነው፡፡››
‹‹ምን …?››ከተቀመጠበት ተነሳ…አፍጥጦ ፎቶውን መመለክት ጀመረ፡፡
በሁኔታው ተበሳጨች….‹‹… ዝም ብዬ እንድታውቀው ስለፈለኩ ነው እንጂ ይሄን ያህል ምን ያስደነግጥሀል…?አታገባኝ ወይ አትወሽመኝ ..አንድ ልጅ ኖረኝ አምስት ምን አጨናነቀህ…?››
በቆመበት አፍጥጦ በዝምታ ያያት ጀመር፡፡ያ ደግሞ የበለጠ ንዴቷን እንዲጨምር አደረገ…‹‹እንደውም ሁሉ ነገር እዚህ ላይ ያብቃ ወደቤቴ ልሂድ››ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ተንደርድሮ መጥቶ ትከሻዋን ይዞ አስቀመጣትና ግንባሯን ሳማት፡፡
‹‹በጣም ነጭናጫ ሴት መሆንሽን ታውቂያለሽ?››
‹‹እንኳን››
‹‹እኔ ይህቺን የመሰለች ልጅ ስላለሽ ቀናሁብሽ እንጂ አልተበሳጨሁበሽም…በጣም እኮ ነው የምታምረው…..ደግሞ በስንት አመትሽ ብትወልጂያት ነው እንዲህ ያደገችው?››
‹‹በ17››
‹‹እና የት ነው ያለችው ..ከአንቺ ጋር ወይስ አባቷ ጋር?››
‹‹አባቷ መፀናሷን እንዳወቀ ነው ሸሽቶ ውትድርና ተቀጥሮ የጠፋው..እስከአሁን ይኑር ይሙት አላውቅም…እሷ ከእኔ ጋር ነው ያለችው፡፡››
‹‹እና አሁን እቤት ነው ያለቻ ?ብንሄድ እናገኛታለን?››
በመገረም አፍጥጣ ተመለከተችው‹‹የእውነት አሁን እንሂድ ብልህ ትሄዳለህ?››
‹‹አዎ..››ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ …‹‹ሰዓቱ ገና ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ከ10 ነው …ተነሽ እንደውም….የሆነ ነገር ገዝተንላት እንሂድ እና እናስደስታት፡፡››
እሱ ጃኬቱን ሲለብስ እሷ ከተቀመጠችበት ሳትንቀሳቀስ በገረሜታ አፏን ከፈተችና በፍዘት ታየው ነበር፡፡
‹‹አልሰማሺኝም እንዴ? ተነሽ እንሂድ››
‹‹ልጅ ማትወድ መስሎኝ ነበር››
በተራው ደነገጠ…‹‹እንዴ ምን ማለት ነው…?እንዴት እንደዛ ልታስቢ ቻልሽ?››
‹‹ቅድም የወንድምህን ልጅ ወደአንተ ይዤ መጥቼ ሳስተዋውቅህ..ከእቅፌ ወስደህ አቅፈህ የምትስመው መስሎኝ ነበር…ግን እንደዛ አላደረክም..ጉንጩን አንኳን አልሳምክም››
ወደእሷ መጣና ከጎኗ ተቀመጠ‹‹ያን ያህል ስትታዘቢኝ ነበር ማለት ነው…?ላቅፈውና ልስመው በጣም ነበር የፈለኩት….አጎትህ ነኝ ብዬ እሽኮኮ በማድረግ ከሆቴሉ ይዤው ወጥቼ ላዝናናው ሁሉ ፈልጌ ነበር..ግን አልቻልኩም…ምክንያቱም የወንድሜ ልጅ ነው ፤ስለወንድሜ ሳስብ ደግሞ በደረቷ ቢላዋ ተሰክቶባት ወለል ላይ የተዘረጋች እናቴና በገመድ የተንጠለጠለች እህቴ ነች ወደአእምሮዬ የምትመጣው…በዛን ወቅት አሰብ የነበረው ስለእነሱ ነበር …እንባዬ እንዳያመልጠኝና በሰርግ እድምተኞች ፊት እንዳልዋረድ እየጣርኩ ነበር››እንባው ከአይኖቹ እየተዘረገፈ መውረድ ጀመረ፡፡ ደነገጠችና ከተቀመጠችበት ተነሳች በእጇቾ እንባውን እበሰችና ግንበሩን ጉንጮቹን እያገላበጠች እየሰማች‹‹ይቅርታ…በጣም ይቅርታ…እኔ እንዲህ አይነት ቀሽም ሴት ነኝ…ሶሪ ወንዶችን ሰላማላምን ሁሉን ነገር ነው የምጠራጠረው…ከልጄ አባት ውጭ ሌላ ወንድ አላውቅም…ከአንተ ጋር በእንደዚህ አይነት መጠን መቀራረብና በአንድ ክፍል ውስጥ መሆን በጣም ቢያስደስተኝም በዛው መጠን አስፈርቶኛል….ለዛ ነው ያልሆነ ነገር የምቀባጥረው፡፡››
‹‹ችግር የለውም… ተረድቼሻለው››
‹‹በቃ በፈጣሪ ያልኩህን ሁሉ እርሳው…››ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት..በጠንካራ እጆቹን በቀጭን ወገቧ ዙሪያ ጠመጠመና ከሰውነት ጋር ለጥፎ ትንፋሽ እስኪያጥራት መጠጣት…..ከዛ ለቀቃትና..‹‹በይ አታረሳሺኝ ተነሽ እንሂድ››
‹‹በእውነት ቢሆንና ብታይህ በጣም ነበር የምትደሰተው…ሙዚቀዎችህን በጣም ነው የምትወዳቸው…ግን አሁን የለችም››
‹‹የለችም ማለት?››
‹‹አሁን ክረምት አይደል..ትምህርት ስለተዘጋ አያቶቾ ወስደዋታል….የሚቀጥለውን አንድ ወር እነሱ ጋር ነው የምታሳለፈው….››
‹‹እ ያሳዝናል…እንግዲህ ምን ማድረግ ይቻላል ስትመለስ ታስተዋውቂኛለሽ››
‹ስትመለስ?››አለችና ሳቀች፡፡
‹‹ምን ያስቅሻል?››
‹‹የዛሬ ወር እኮ ነው ያልኩህ…››
‹‹ምነው የዛሬ ወር የለሁም እንዴ..?አለሁ እኮ ፤ማለቴ በፍቅርሽ አሟሙተሸ ካላጠፋሺኝ አለው..››
‹‹ይሁን እስኪ…..ለማንኛውም አስገርመሀኛል››አለችና የመጠጡን ብርጭቆ አነስታ ተጎነጨች፡፡
‹‹እድሉን እስከሰጠሺን ድረስ ገና ብዙ አሰግርምሻለው፡፡››
ከዛ ቀልል ያለ ወሬ እያወሩ ከመጠጡ መጎንጨታቸውን ቀጠሉ….
‹‹ይሞቃል አይደል?››አለችው የእውነትም በጣም እየሞቃት ነው…ያላወቀችው የሙቀቱ ምንጭ ከምትጠጣው መጠጥ ይመንጭ ወይም ከጎኗ ካለው ሸበላ ወይም ከአየር ፀባዩ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡
‹‹እኔም ሞቋኛል …››አለና ጃኬቱን አወለቀ፡፡
‹‹እኔስ ቀሚሴን ላውልቅ?››አለችውና ሳቀች፡፡
‹‹ይቻላል..ቆይ እንደውም..›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ወደሻንጣው በመሄድ ከፈተው፡፡ምን ሊያደርግ ነው ብላ በትኩረት እየተከታተለችው ነው፡፡
ስስ ቁምጣ እና ቲሸርት አወጣና…እንቺ ቀሚሱን አውልቂና ይሄን ልበሺ አለና ለራሱ ሌላ ቢጃማ በማውጠት ሱሪውን ለማውለቅ ቀበቷውን መፍታት ጀመረ፡፡
‹‹ምን እያደረክ ነው?››
‹‹ሱሬዬን ልቀይር ነዋ….››
ሱሪውን ወደታች አወለቀ..ከዛ ከላይ የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ..በነጭ ፓካውትና በሰማያዊ ፓንት ብቻ በሁለት ሜትር ርቀት ቆሞ ስትመለከት ሰውነቷን ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ነገር አንዘረዘራት፡፡በልብስ ከሚታየው ይልቅ እርቃኑን ያምራል…ደግሞ ከፊል ሰውነቱ በተለያዩ ማራኪ ንቅሳቶች የተዥጎረጎረ ነው፡፡
‹‹ምነው ፈዘዝሽ?››ብሎ አሳፈራት፡፡
‹‹ምን ፈዛለው…እንደ ሸራ በስእል ተዥጎርጉረህ የለ እንዴ?››
የሚቀይረውን ቢጃማ ሱሪ አነሳና በእጁ እንደያዘ‹‹ያምራል አይደል…?እስኪ በደንብ ተመልከቺው ››አለና ይበልጥ ወደእሷ ተጠጋና ስሯ ቆመ፡፡
ዝም አለች ..ጎትቶ አስነሳት‹‹እንዴ ምን እያደረክ ነው?››
እጇቾን ያዘና ደረቱ ላይ አሳረፈ…ዝም ብላ ታዘዘችለት…እጁን ወደታች አወረደና ቀሚሷን ወደላይ ሳበ‹‹ምን…..?››ንግግሯን ሳትጨርስ አፉን አፋ ላይ ከደነ….እጇቾን ጠመጠመችበትና በንቅሳት የተዝጎረጎረ ጀርባውን መዳበስ ጀመረች ..ከዛ እሱ እጆቾን ያዘና ቀሚሷ ወደ ላይ ሞሽልቆ አንገቷ ጋር አደረሰ..ከዛ ከንፈሩን ከከንፈሯ አላቀቀና ወደላይ አወለቀላና ከእሷ ሁለት ሜትር ወደኃላ ራቀ…..በእፍረት ሽምቅቅ አለች‹‹‹ምን ያህል ውብ እንደሆንሽ ታውቂያለሽ ግን….?በተለይ እግሯችሽ ››
‹‹ምን አይነት ሰው ነህ..?››ብላ አውልቆ የጣለውን ቀሚስ ለመልበስ መልሳ አነሳች…‹‹ቆይ ቆይ››ዘሎ መጥቶ ነጠቃትና ያወጣላትን ቲሸርትና ቁምጣ አቀበላት፡፡ ተቀበለችውና ቆመች…ልልበስ ይቅርብኝ ብላ ሙግት ውስጥ የገባች ይመስላል፡፡
‹‹እንደታጠበ ነው..አለበስኩትም››
ዝም ብላ መልበስ ጀመረች፡፡
እንደ ሞኝ በብዙ አይነት ጥርጣሬዎች በውስጦ ስለታጨቁ ተጨናንቃለች፡፡ በዚህ ጉዳይ በጣም አሳፈሪ ብትሆንስ? ስህተት ብትሠራስ? በመካከላቸው ያለው አካላዊ ኬሚስትሪ በጣም ቀላል ፣ በጣም ተፈጥሯዊ እናም በጣም ትክክለኛ ይመስል ነበር። አሁን ግን በሆቴሉ መኝታ ቤቱ ደማቅ ብርሃን ስር፣ ሰውነቱ በግልፅ እየተመለከተች ሁኔታውን በምልሰት ስትገመግመው እንደአሰበችው ቀላል አይመስልም።ስለ ወሲብ ምንም አታውቅም። ላለፉት ስድስት ዓመታት ምንም አይነት ፍቅር አልሰራችም እና ስለ እንደዚህ አይነት ስሜት ላይ የተንጠለጠለ አጭር ግንኙነት የምታስታውሰው ምንም ነገር ስለሌለ እንደ ዘሚካኤል ካለ ሰው ጋር እንድትተኛ አላዘጋጃትም።
‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 መግባት አለበት ይሄ ድርሰት እስከሚያልቅ
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ምን አይነት ሰው ነህ..?››ብላ አውልቆ የጣለውን ቀሚስ ለመልበስ መልሳ አነሳች…‹‹ቆይ ቆይ››ዘሎ መጥቶ ነጠቃትና ያወጣላትን ቲሸርትና ቁምጣ አቀበላት፡፡ ተቀበለችውና ቆመች…ልልበስ ይቅርብኝ ብላ ሙግት ውስጥ የገባች ይመስላል፡፡
‹‹እንደታጠበ ነው..አለበስኩትም››
ዝም ብላ መልበስ ጀመረች፡፡
እንደ ሞኝ በብዙ አይነት ጥርጣሬዎች በውስጦ ስለታጨቁ ተጨናንቃለች፡፡ በዚህ ጉዳይ በጣም አሳፈሪ ብትሆንስ? ስህተት ብትሠራስ? በመካከላቸው ያለው አካላዊ ኬሚስትሪ በጣም ቀላል ፣ በጣም ተፈጥሯዊ እናም በጣም ትክክለኛ ይመስል ነበር። አሁን ግን በሆቴሉ መኝታ ቤቱ ደማቅ ብርሃን ስር፣ ሰውነቱ በግልፅ እየተመለከተች ሁኔታውን በምልሰት ስትገመግመው እንደአሰበችው ቀላል አይመስልም።ስለ ወሲብ ምንም አታውቅም። ላለፉት ስድስት ዓመታት ምንም አይነት ፍቅር አልሰራችም እና ስለ እንደዚህ አይነት ስሜት ላይ የተንጠለጠለ አጭር ግንኙነት የምታስታውሰው ምንም ነገር ስለሌለ እንደ ዘሚካኤል ካለ ሰው ጋር እንድትተኛ አላዘጋጃትም።
‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 መግባት አለበት ይሄ ድርሰት እስከሚያልቅ
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡
ይህ ምሽት ከዘሚካኤል ጋር በፍቅር ከመውደቅ ጋር ወይም ከእሱ ጋር የወደፊት ከህልም ከማለም ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። እና ሁሉም ነገር የሚከናወነው ለአካላዊ ደስታ ብቻ ተብሎ ነው። የልጅነት ፍቅረኛዋ ለዚህ ሁሉ አመታት የሆነ ነገሯን ሰርቆባታል እና አሁን ሊመልስላት ይገባል ። እና ጉዳዩ ያ ብቻ ነበር።
ጠረጴዛ ላይ ያለው ብርጭቆ አነሳና ከተጎነጨለት በኋላ እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነባት ፡፡
፤ዝም አለች…እጁን በአንገቷ ዙሪያ አሻግሮ በቲሸርቱ ስር አሾለከና ወደጡቷ መጓዝ ጀመረ..ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹ዘና በይ እንጂ። ይህ ለሁለታችንም ጥሩ ይሆናል፣ ቃል እገባልሻለው።›› መልሶ እጁን አወጣና ወደአልጋው ላይ ቀድሟት በመውጣት እጇን ይዞ ወደ አልጋው እየሳበ ።
‹‹ተነሽ በቃ እንተኛ። ››አላት፡፡
ዝም ብላ ተጎተተችለትና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋው ላይ ወጣች ።መናገር አልቻለችም፣ የልቧ ፈጣን ምቶች በጉሮሮዋ ላይ ተስፈንጥረው ሚወጡ ይመስላሉ።ወደራሱ ሳበና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡እና እጆቹን ፀጉሯ ውስጥ አስገባና ይልግላት ጀመር…ከመደንዘዞ የተነሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡ከዛ አንገቷን ..ጆሮዋን መሳም ጀመረ …ቃተተች.፡፡ወደታች ዝቅ አለና ቲሸርቷን ገለጠና ከእንብርቷ ጀምሮ እየላሰ ወደላይ ወጣ…ጡቶቾ ጋር ደረሰ የቀኝ ጡቷን ጫፍ በምላሱ እየላሰ የግራውን ጡቷን በእጆቹ እየጨመቀ ያፍተለትላት ጀመር…በፈጣሪ… እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን በፍፁም አታውቅም….ጡት ለተሳማ እንዴት ነው መላ ሰውነት እንዲህ ቀልጦ የሚንሳፈፈው…?.በጣም ያስገረማት ጉዳይ ነው፡፡
‹‹ እሺ በቃ አሁን….››ተንተባተበችና እንደምንም ጨክና ከጡቷ አላቀቀችው
‹‹እስከ ሞት ድረስ የፈራሽ ትመስያለሽ። ምንድነው ችግሩ?፧››ሲላት እንደምንም እያጎለበተችው የነበረው ትንሹ ድፍረት ጥሏት ሄደ…ይሄንን ደግሞ እሱም በግልፅ ማየት ይችላል…፡፡
‹‹መብራቶቹን ማጥፋት እንችላለን?››ብላ በሹክሹክታ ጠየቀችው።
‹‹አላደርገውም።…ውብ እርቃኗን ለማያት ለቀናት ስለእሷ ሳሰላስል የሰነበትኩላትን ልጅ ሳገኛት …በጭለማ….አይ አይሆንም ..አንቺን ለማግኘት ያን ሁሉ ጥረት የጣርኩት በጨለማ ውስጥ ፍቅር ለመስራት አይደለም።››ተቃወማት፡፡
ጡቶቿ ትንሽ ነበሩ፣ ዳሌዋ ጠባብ እና የልጅ ነበር። ጉንጯን ነካ፣ በዓይኑ ያልጠበቀችው ልስላሴ እና ፈገግታ ተመለከተች። ' ለመቃወም አፏን ከፈተች እሱ ግን ጣቱን ከንፈሯ ላይ አሳረፈ።‘
‹‹አትልፊ አልስማማም››አለና የዋናውን መብራት ማብሪያ / ማጥፊያ ለማጥፋት አልጋውን ለቅቆ ወረደ , ደማቁን ብርሀን ቢወገድም አረንጓዴና ደብዛዛ ብርሀን ግን አሁንም ቤቱን እንደሞላው ነው፡፡ ከላይ የለበሰውን ካኔቴራ አወለቀና እርቃኑን ወደአላጋው ላይ ወጣ…..እና ቆመ….‹‹ምነው ቁጭ በል እንጂ››
…
የለበሰውን ቁምጣ ከነፓንቱ አንድ ላይ መዥርጦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….እንደሀውልት የተገተረው እንትኑ አይኗቾን ተቆጣጠረ…..የበለጠ በፍርሀት ተንዘረዘረች፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንዴ ምን ሰራለሁ.. ልንተኛ አይደል ….?ብርድልብሱን እና አንሶላውን ገለጠና ከውስጥ ገባ…
.‹‹አውልቀሽ ወደእኔ ትመጪያለሽ ወይስ…..?››
ምንም መናገር አልቻለችም….ዝም አለች፡፡‹‹ምንም ልምድ የለሽም አይደል?››ሲል ጠየቃት፡፡፡
‹‹ልክ ነህ። በዚህ ረገድ ብዙ ልምድ የለኝም። እንደውም እውነቱ ለመናገር እኔ ምንም አይነት ልምድ የለኝም ›› አለችው ። ማስመሰል ምን ፋይዳ አልነበረው? ከአመታት በፊት ካጋጠማት ከዛ አስጸያፊ ምሽት ገጠመኞ በኋላ በእድሜ ጨምራ እና በስሜት ጎልምሳ ሊሆን ይችላል… ግን ያ በቂ አይሆንም። ለዛውም እንደ ዘሚካኤል አይነት ከሴት ጋር ባለው ልምድ የበለፀገ አይነት ሰውን ለመቋቋም ፈጽሞ እንደማትችል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹ከብዙ ልምድ ያላቸው ሴቶች ጋር ተኝተሀል ..እና ከእኔ ጋር በምታደርገው ነገር ቅር መሰኘትህ አይቀርም ፣ ››ብላ ጨረሰች ።ሙሉ በሙሉ ተሸነፈች።
‹‹ ውዴ ፣ ስለ እንደዛ አይነት ነገር ፈፅሞ መጨነቅ አያስፈልግሽም -ሁሉን ነገር አብረን በዝግታና በትግስት እናደርገዋለን….እኔ አንቺን ከማንም ጋር ላወዳድርሽ ሀሳብ የለኝም….›› የእሱ አጽናኝና አበረታች ቃላት ጉዳቷን እና ውርደቷን ትንሽ አጠበላት።ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይህ ፈተና አይደለም.›› ጎተተና ወደውስጥ ስቦ አስገባት፡፡ከዛ ቀስ አለና ቲሸርቷን ወደላይ ስቦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….ከዛ ወደኋላ አጋዳማትና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡
‹‹እንግዲህ እጅ ሰጥቻለው…ችግር የለውም ካልክ….እንደፈለክ አድርገኝ››በማለት ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠቷን በይፋ አወጀች፡፡
‹‹ ውዴ አፈጻጸም ላይ ጭንቀት ካለብሽ ለምንድነው ለተወሰነ ጊዜ ሂደቱን የማትመሪው?››የሚል አስገራሚ ሀሳብ አቀረበላት፡፡
በድንገት መተንፈስ አቃታት።
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ..?ጭራሽ መምራት…‹‹በል የምታደርገውን እንደፈለግክ አድርግ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ደግሞ እኔም አንቺ የምታስቢውን ያህል ጎበዝ ላልሆን እችላለው ›› ብሎ ቀጠለ፣ በብልህ ጣቶቹን ጡቷቿን እያፍተለተለ ነው፡ ፡ቃተተች፡፡እሱ ሹክሹክታ በመሰለ ድምፅ መናገሩን ቀጠለ፡፡
ተንቀጠቀጠች፡፡ከአንገቷ ጀምሮ ወደታች ይልሳት ጀመር …ሳታስበው ሰውነቱ ላይ ተጣበቀችበት….ከታች እንትኑ ክፉኛ ቆረቆራት..ደስ የሚል መቆርቆር….የሚበላ እና ሚያሳክክ አይነት መቆርቆር …እሱም እንደተመቻት ስለገባው ይሰመስላል… በጠንካራ ጡንቻው ሰቅስቆ ወደራሱ አጥብቆ መሳሙን ቀጠለ….እያንዳንዷ የሚስማት ቦታ ልዩ አይነት የተለያየ ጣእም ያለው መስሎ ተሰማት…..ለዘመናት እንደዛ እየሳማት እንዲቆይ ተመኘች….እየቀለጠች ነው….ሆዷና ጀርባዋ በላብ እየታጠበ ነው፡፡እጁን ወደታች ሰደደና በለበሰችው ቁምጣዋንና ፓንቷን ሰቅስቆ ገባ……..‹‹ወይኔ ጉዴ ምን ሊያደርግ ነው?››አሰበች …የእጁን መዳፍ ብልቷ ላይ አሳረፈ……ድምፅ አውጥታ ማቃሰት ጀመረች….ከላዮ ላይ ተነሳና ቀና ብሎ የለበሰችውን ቁምጣን ፓንቷን አንድ ላይ ይዞ ወደታች ጎትቷ ማውለቅ ጀመረ…እግሯን ወደላይ ከፍ በማድረግ ተባበረችው፡፡ወደ ሰውነቱ አጥብቆ አቀፋትና ከጆሮዋ አንስቶ አንገቷን መሳም ጀመረ….ተቁነጠነጠች፡፡ቀስ እያለ መሳሙንም መዳበሱንም ሳያቋርጥ ወደታች ሄደ… ከዛ አንገቱን እግሯቾ መካከል ደፈቀ….ለፈለፈች….በመላ ሰውነቷ ቤንዚል ተርከፍክፎ ክብሪት የተጫራባት ነው የመሰላት…እጆቾን ፀጉሩ ላይ አድርጋ ታሻሸው ጀመር…ቀስ አለና እየሳማት ወደላይ መጓዝ ጀመረ… ከንፈሯ ጋር ሲደርስ ቀድማ ተጣበቀችበት….ሙሉ በሙሉ እግሮቾን መካከል ገብቷ ተዋሀዳት….ልዩ ጣፋጭነት ያለው ስቃይ ተሰማት…ስቃዩ እንዲያቆም ግን ፈፅሞ አትፈልግም…ይበልጥ መቃተት ይበልጥ መሰቃየት ፈልጋለች፡፡ሁለቱም እኩል ከፍተኛ ፍንዳታ ላይ ደረሱ አደኛው ሌለኛውን ወደራሳቸው ጨምቀው አቀፉ..ተርገፈገፉ…..በመከራ ተላቀቁና ጎን ለጎን ተዘረሩ፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ወደእሷ ዞረና‹‹እንዴት ነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አረ…እንዲህ አይነት ጉብዝና መኖሩን እራሱ የት አውቃለው?››አለችው፡፡
ግንባሩን ወደ እርስዋ አስጠጋ ፣በረጅሙ ተነፈሰች።‹‹የእኔ ቆንጆ ሁለነገርሽ እንደሚያምር ታውቂያለሽ አይደል?...አይዞሽ ሁሉ ነገር ልዩ ይሆናል…ወደፊት ብዙ የምትማሪው ነገር ሊኖር ይችላል›› አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡
ይህ ምሽት ከዘሚካኤል ጋር በፍቅር ከመውደቅ ጋር ወይም ከእሱ ጋር የወደፊት ከህልም ከማለም ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። እና ሁሉም ነገር የሚከናወነው ለአካላዊ ደስታ ብቻ ተብሎ ነው። የልጅነት ፍቅረኛዋ ለዚህ ሁሉ አመታት የሆነ ነገሯን ሰርቆባታል እና አሁን ሊመልስላት ይገባል ። እና ጉዳዩ ያ ብቻ ነበር።
ጠረጴዛ ላይ ያለው ብርጭቆ አነሳና ከተጎነጨለት በኋላ እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነባት ፡፡
፤ዝም አለች…እጁን በአንገቷ ዙሪያ አሻግሮ በቲሸርቱ ስር አሾለከና ወደጡቷ መጓዝ ጀመረ..ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹ዘና በይ እንጂ። ይህ ለሁለታችንም ጥሩ ይሆናል፣ ቃል እገባልሻለው።›› መልሶ እጁን አወጣና ወደአልጋው ላይ ቀድሟት በመውጣት እጇን ይዞ ወደ አልጋው እየሳበ ።
‹‹ተነሽ በቃ እንተኛ። ››አላት፡፡
ዝም ብላ ተጎተተችለትና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋው ላይ ወጣች ።መናገር አልቻለችም፣ የልቧ ፈጣን ምቶች በጉሮሮዋ ላይ ተስፈንጥረው ሚወጡ ይመስላሉ።ወደራሱ ሳበና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡እና እጆቹን ፀጉሯ ውስጥ አስገባና ይልግላት ጀመር…ከመደንዘዞ የተነሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡ከዛ አንገቷን ..ጆሮዋን መሳም ጀመረ …ቃተተች.፡፡ወደታች ዝቅ አለና ቲሸርቷን ገለጠና ከእንብርቷ ጀምሮ እየላሰ ወደላይ ወጣ…ጡቶቾ ጋር ደረሰ የቀኝ ጡቷን ጫፍ በምላሱ እየላሰ የግራውን ጡቷን በእጆቹ እየጨመቀ ያፍተለትላት ጀመር…በፈጣሪ… እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን በፍፁም አታውቅም….ጡት ለተሳማ እንዴት ነው መላ ሰውነት እንዲህ ቀልጦ የሚንሳፈፈው…?.በጣም ያስገረማት ጉዳይ ነው፡፡
‹‹ እሺ በቃ አሁን….››ተንተባተበችና እንደምንም ጨክና ከጡቷ አላቀቀችው
‹‹እስከ ሞት ድረስ የፈራሽ ትመስያለሽ። ምንድነው ችግሩ?፧››ሲላት እንደምንም እያጎለበተችው የነበረው ትንሹ ድፍረት ጥሏት ሄደ…ይሄንን ደግሞ እሱም በግልፅ ማየት ይችላል…፡፡
‹‹መብራቶቹን ማጥፋት እንችላለን?››ብላ በሹክሹክታ ጠየቀችው።
‹‹አላደርገውም።…ውብ እርቃኗን ለማያት ለቀናት ስለእሷ ሳሰላስል የሰነበትኩላትን ልጅ ሳገኛት …በጭለማ….አይ አይሆንም ..አንቺን ለማግኘት ያን ሁሉ ጥረት የጣርኩት በጨለማ ውስጥ ፍቅር ለመስራት አይደለም።››ተቃወማት፡፡
ጡቶቿ ትንሽ ነበሩ፣ ዳሌዋ ጠባብ እና የልጅ ነበር። ጉንጯን ነካ፣ በዓይኑ ያልጠበቀችው ልስላሴ እና ፈገግታ ተመለከተች። ' ለመቃወም አፏን ከፈተች እሱ ግን ጣቱን ከንፈሯ ላይ አሳረፈ።‘
‹‹አትልፊ አልስማማም››አለና የዋናውን መብራት ማብሪያ / ማጥፊያ ለማጥፋት አልጋውን ለቅቆ ወረደ , ደማቁን ብርሀን ቢወገድም አረንጓዴና ደብዛዛ ብርሀን ግን አሁንም ቤቱን እንደሞላው ነው፡፡ ከላይ የለበሰውን ካኔቴራ አወለቀና እርቃኑን ወደአላጋው ላይ ወጣ…..እና ቆመ….‹‹ምነው ቁጭ በል እንጂ››
…
የለበሰውን ቁምጣ ከነፓንቱ አንድ ላይ መዥርጦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….እንደሀውልት የተገተረው እንትኑ አይኗቾን ተቆጣጠረ…..የበለጠ በፍርሀት ተንዘረዘረች፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንዴ ምን ሰራለሁ.. ልንተኛ አይደል ….?ብርድልብሱን እና አንሶላውን ገለጠና ከውስጥ ገባ…
.‹‹አውልቀሽ ወደእኔ ትመጪያለሽ ወይስ…..?››
ምንም መናገር አልቻለችም….ዝም አለች፡፡‹‹ምንም ልምድ የለሽም አይደል?››ሲል ጠየቃት፡፡፡
‹‹ልክ ነህ። በዚህ ረገድ ብዙ ልምድ የለኝም። እንደውም እውነቱ ለመናገር እኔ ምንም አይነት ልምድ የለኝም ›› አለችው ። ማስመሰል ምን ፋይዳ አልነበረው? ከአመታት በፊት ካጋጠማት ከዛ አስጸያፊ ምሽት ገጠመኞ በኋላ በእድሜ ጨምራ እና በስሜት ጎልምሳ ሊሆን ይችላል… ግን ያ በቂ አይሆንም። ለዛውም እንደ ዘሚካኤል አይነት ከሴት ጋር ባለው ልምድ የበለፀገ አይነት ሰውን ለመቋቋም ፈጽሞ እንደማትችል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹ከብዙ ልምድ ያላቸው ሴቶች ጋር ተኝተሀል ..እና ከእኔ ጋር በምታደርገው ነገር ቅር መሰኘትህ አይቀርም ፣ ››ብላ ጨረሰች ።ሙሉ በሙሉ ተሸነፈች።
‹‹ ውዴ ፣ ስለ እንደዛ አይነት ነገር ፈፅሞ መጨነቅ አያስፈልግሽም -ሁሉን ነገር አብረን በዝግታና በትግስት እናደርገዋለን….እኔ አንቺን ከማንም ጋር ላወዳድርሽ ሀሳብ የለኝም….›› የእሱ አጽናኝና አበረታች ቃላት ጉዳቷን እና ውርደቷን ትንሽ አጠበላት።ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይህ ፈተና አይደለም.›› ጎተተና ወደውስጥ ስቦ አስገባት፡፡ከዛ ቀስ አለና ቲሸርቷን ወደላይ ስቦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….ከዛ ወደኋላ አጋዳማትና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡
‹‹እንግዲህ እጅ ሰጥቻለው…ችግር የለውም ካልክ….እንደፈለክ አድርገኝ››በማለት ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠቷን በይፋ አወጀች፡፡
‹‹ ውዴ አፈጻጸም ላይ ጭንቀት ካለብሽ ለምንድነው ለተወሰነ ጊዜ ሂደቱን የማትመሪው?››የሚል አስገራሚ ሀሳብ አቀረበላት፡፡
በድንገት መተንፈስ አቃታት።
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ..?ጭራሽ መምራት…‹‹በል የምታደርገውን እንደፈለግክ አድርግ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ደግሞ እኔም አንቺ የምታስቢውን ያህል ጎበዝ ላልሆን እችላለው ›› ብሎ ቀጠለ፣ በብልህ ጣቶቹን ጡቷቿን እያፍተለተለ ነው፡ ፡ቃተተች፡፡እሱ ሹክሹክታ በመሰለ ድምፅ መናገሩን ቀጠለ፡፡
ተንቀጠቀጠች፡፡ከአንገቷ ጀምሮ ወደታች ይልሳት ጀመር …ሳታስበው ሰውነቱ ላይ ተጣበቀችበት….ከታች እንትኑ ክፉኛ ቆረቆራት..ደስ የሚል መቆርቆር….የሚበላ እና ሚያሳክክ አይነት መቆርቆር …እሱም እንደተመቻት ስለገባው ይሰመስላል… በጠንካራ ጡንቻው ሰቅስቆ ወደራሱ አጥብቆ መሳሙን ቀጠለ….እያንዳንዷ የሚስማት ቦታ ልዩ አይነት የተለያየ ጣእም ያለው መስሎ ተሰማት…..ለዘመናት እንደዛ እየሳማት እንዲቆይ ተመኘች….እየቀለጠች ነው….ሆዷና ጀርባዋ በላብ እየታጠበ ነው፡፡እጁን ወደታች ሰደደና በለበሰችው ቁምጣዋንና ፓንቷን ሰቅስቆ ገባ……..‹‹ወይኔ ጉዴ ምን ሊያደርግ ነው?››አሰበች …የእጁን መዳፍ ብልቷ ላይ አሳረፈ……ድምፅ አውጥታ ማቃሰት ጀመረች….ከላዮ ላይ ተነሳና ቀና ብሎ የለበሰችውን ቁምጣን ፓንቷን አንድ ላይ ይዞ ወደታች ጎትቷ ማውለቅ ጀመረ…እግሯን ወደላይ ከፍ በማድረግ ተባበረችው፡፡ወደ ሰውነቱ አጥብቆ አቀፋትና ከጆሮዋ አንስቶ አንገቷን መሳም ጀመረ….ተቁነጠነጠች፡፡ቀስ እያለ መሳሙንም መዳበሱንም ሳያቋርጥ ወደታች ሄደ… ከዛ አንገቱን እግሯቾ መካከል ደፈቀ….ለፈለፈች….በመላ ሰውነቷ ቤንዚል ተርከፍክፎ ክብሪት የተጫራባት ነው የመሰላት…እጆቾን ፀጉሩ ላይ አድርጋ ታሻሸው ጀመር…ቀስ አለና እየሳማት ወደላይ መጓዝ ጀመረ… ከንፈሯ ጋር ሲደርስ ቀድማ ተጣበቀችበት….ሙሉ በሙሉ እግሮቾን መካከል ገብቷ ተዋሀዳት….ልዩ ጣፋጭነት ያለው ስቃይ ተሰማት…ስቃዩ እንዲያቆም ግን ፈፅሞ አትፈልግም…ይበልጥ መቃተት ይበልጥ መሰቃየት ፈልጋለች፡፡ሁለቱም እኩል ከፍተኛ ፍንዳታ ላይ ደረሱ አደኛው ሌለኛውን ወደራሳቸው ጨምቀው አቀፉ..ተርገፈገፉ…..በመከራ ተላቀቁና ጎን ለጎን ተዘረሩ፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ወደእሷ ዞረና‹‹እንዴት ነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አረ…እንዲህ አይነት ጉብዝና መኖሩን እራሱ የት አውቃለው?››አለችው፡፡
ግንባሩን ወደ እርስዋ አስጠጋ ፣በረጅሙ ተነፈሰች።‹‹የእኔ ቆንጆ ሁለነገርሽ እንደሚያምር ታውቂያለሽ አይደል?...አይዞሽ ሁሉ ነገር ልዩ ይሆናል…ወደፊት ብዙ የምትማሪው ነገር ሊኖር ይችላል›› አላት፡፡
እሷም ግድ አልነበራትም። ወደፊት የሚባል ነገር እሷ አእምሮ ውስጥ ባይኖርም አሁን ግን ሁሉን ነገር በፍጥነት መማር ትፈልግ ነበር፣ እና እሱ እንዲያስተምራት ፍቃደኛ ነች።
‹‹አመሰግናለሁ››አለችው።‹‹በጣም አመሰግናለሁ። ይህንን አይነት እርካታ የጠበኩት አይደለም...›› ትንፋሽ የሌለው ሳቅ ሳቀች፣ ‹‹ይህን ያህል ጥሩ ይሆናል ብዬ አልጠበኩም ነበር››በማለት ግልፅ ሆነችለት፡፡
‹‹እኔን ማመስገን አያስፈልገሽም››አለ፡፡ እጇን በእጁ ይዞ ጣቷን እየሳመ ‹‹አሁን ሽልማቴን ለማግኘት እያሰብኩ ነው።››ሲል አከለበት፡፡
‹‹ማለት የምን ሽልማት?፡፡››
‹‹ስለ ሁለተኛ ዙር ምን ትያለሽ?›› አላት፡፡
‹እንደ መጀመሪያው ዙር ጥሩ ከሆነ..ደስ ይለኛል›› አለችው፡፡ያልጠበቀውና …ደስ ያሰኘው መልስ ነበር፡፡
‹‹እንደውም ከመጀመሪያውም የተሻለ እንዲሆን የተቻለኝን አደርጋለሁ››አላትና ድፍረት የታከለበት ቃል ገባላት፡፡ከዛ በትዕግስት እየጸለየ ወገቧን ይዞ ወደ ስር ጎተታት።ትኩር ብላ ተመለከተችው፣ በደረቷ አስተኛትና ከላዮ ወጣ…አይኖቾ ፈጠጡ..የእውነትም ቃል እንደገባላት በጣም ጣፋጭና ማራኪ ነበር፡፡ግን በጣም እያመማት ነው…እንደውም የተላጠችና የደማች እየመሰላት ነው፡፡እንደዛም ሆኖ አቁም በቃኝ ልትለው ፍላጎት አልነበራትም፡፡አንባዋ ሲንጠባጠብና አንሶላውን ሲያረጥበው ተመለከታት…እሱም ላብ በግንባሩ ችፍ እያለ‹‹አሁን ለቅሷ ጥሩ ምልክት ነው ወይስ መጥፎ?›› ብሎ ጠየቃት ፡፡
በተሰባበረ ድምፅ ‹‹ጥሩ ነው።በጣም ጥሩ…ደስ ብሎኝ ነው ።››አለችው፡፡
ድምፁ ፍፅም እርካታንና ደስታን የሚያንፀባርቅ ነው፡፡ ‹‹ደስ ስላለሽ ደስ ብሎኛል››አላት
፡፡ጠንከር ባለ መልኩ ከሱ ስር ተጣበቀች።ግፊቶች እየጠነከሩ እና ፈጣን እና የበለጠ የማያቋርጥ ሆነዋል። የደስታው ፍንዳታ እንደድንገተኛ ማዕበል በውስጧ ሲስገመገም ይሰማታል…አጓራች ። በመጨረሻው የእርካታ ጫፍ ላይ ስትወጣ ከፍተኛ ህመም እና በቃላት ሊገለጽ የማይችል ደስታ አጥለቀለቃት፡፡ ሁለቱም ሻወር ገብተው ታጥበው ወደአልጋቸው ከተመለሱ በኃላ
‹‹ታዲያ፣ አሁን ከአስር ውጤት ለመስጠት ዝግጁ ነሽ?›› ሲል ጠየቃት።
ልታፈር ይገባ ነበር፣ ነገር ግን በጣም ደንዝዛለች፤ በጣም ረክታለች፣ ስለ ራሷ በጣም ጥሩ ነገር ተሰምቷት፡፡ ‹‹ከዘጠኝ በታች የምትሰጪኝ ከሆነ ማወቅ አልፈልግም››አላት፡፡
በሳቅ እየተንከተከተች ‹‹ከአሥሩ አሥር እንዳገኘህ አስባለሁ››አለችው፡፡
በደስታ ሳቀና ‹‹ግን አሳመምኩሽ እንዴ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ፣ አላመመኝም››አለች ፡፡በራሷ መልስ እፍረት ተሰማት፡፡ከዚህ ሰው ጋር ምንም አይነት ቅርርብ ውስጥ ልትወድቅ አትችልም። ያደረጉት ነገር ከአንድ የደስታ ምሽት ያለፈ ትርጉም ሊኖረው አይችልም። ያንን አውቃለች። እሱ ከእርሷ ደረጃ በጣም ሩቅ ነበር ፣
እጁን ዘርግቶ በመደገፍ ጣቶቹን በጣቶቿ ውስጥ አቆላለፈ። ወደጆሮዋ ተጠጋና በሹክሹክታ ‹‹በጣም ጣፋጭ ነሽ የእኔ ቆንጆ››አላት
…‹‹ጨካኝ ድምፁ ከማንኛውም መድሃኒት የበለጠ ሱስ ያሲይዛል።››ስትል በውስጦ አሰበች፡፡
እንቅልፍና ድካም ተጋግዘው አዛሏት ፡፡ እግሮቿ ማራቶን እንደሮጠ ሰው ይመስል በጣም ተዝለፍልፈዋል። እጇን ዘረጋች። አይኖቾን ጨፈነች…ግን ከመተኛት ይልቅ በሀሳብ ተዋጠች፡፡
ዘሚካኤል ሁል ጊዜ ከወሲብ በኋላ መተቃቀፍን አይፈልግም ነበር፡፡ይህ የተለመደና የቆየ ልማዱ ነው…ከወሲብ በኃላ የአልጋውን ጠርዝ ይዞና ፊቱን በሴቲቱ በተቃራኒው ካልዞረ ምቾትም አይሰማውም.. እንቅልፍም አይወስደውም ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አሁን እሷን ሰውነቱ ላይ ለጥፎ ክንዱ ላይ አስተኝቶ ትንፋሿን እየማገ ለመተኛት ፈቀደ…. ? ለዛውም ደስ እያለው..ላዛውም ምቾት እየተሰማው..?‹‹ይህቺ ልጅማ የሆነ እስከአሁን በውል ያልተገነዘብኩት አንድ የተለየ ነገር አላት››ሲል አሰበ፡፡
እሷም በተመሳሳይ ሁኔታ ስለሰሩት ፍቅራና እያሰላሰለች ነበር፡፡ ከስድስት ዓመታት በፊት ተመሳሳይ ገጠመኝ አጋጥሟት ነበር፣ ያ ግን ደስ የማይል ነገር ነበር።በወቅቱ ያንን ወሲብ የፈጸመችው ምንም አይነት ፍላጎት ሳይኖራት ነበር፡፡እርግጥ ፍቅረኛዋን አምርራ ትወደው ነበር….እና እሱ በወቅቱ ክፍኛ ፈልጎ ስለነበር እሱን ላለማስቀየምና በዛ ተማሮ እንዳይተዋት በመፍራት ፈቀደችለት….አደረጉ …ለእሷ የተረፋት ልብ የሚሰነጥቅ ህመምና አንሶላ ሚያቀልም ደም ብቻ ነበር፡፡ እና እንደዛም ሆኖ እሱን ማጣቷ አልቀረም ነበር፡፡እና ከሁለት ያጣች ሆነች፡፡ከዛም አልፎ አረገዘች፡፡እና በእንደዛ አይነት የተደራረበ ምክንያት ወሲብ የሚባል ነገር በሀሳብ ደረጃ እንኳን ወደአእምሮዋ ብልጭ እንዳይል መታገል ጀመረች፡፡እናም ለስድስት አመት እራሷን ማቀብ ተሳካላት፡፡ ለምን ሌላ እሷ ለረጅም ጊዜ ያለ ወሲብ ትሄዳለች? ግን እሷ ጋር መተኛት ለእሱ አስፈላጊ የሆነው ለምንድነው? ኃላፊነት የሚሰማውስ ለምንድን ነው? ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት እየባተተች እንቅልፍ ይዞት ጥርግ አለ….እሱም ወዲያው እሷን ተከትሎ ተኛ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 ለመግባት #63 ሰው ብቻ ይቀራል በነገራችን ላይ በአንድ ቀን ሊሞላ የሚችል ነገር ነበር ግን አልሆነም በተቻላቹ አቅም subscriber እያደረጋቹ ቤተሰቦች
ለሁሉም በቅድሚያ አመሰግናለሁ👍
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹አመሰግናለሁ››አለችው።‹‹በጣም አመሰግናለሁ። ይህንን አይነት እርካታ የጠበኩት አይደለም...›› ትንፋሽ የሌለው ሳቅ ሳቀች፣ ‹‹ይህን ያህል ጥሩ ይሆናል ብዬ አልጠበኩም ነበር››በማለት ግልፅ ሆነችለት፡፡
‹‹እኔን ማመስገን አያስፈልገሽም››አለ፡፡ እጇን በእጁ ይዞ ጣቷን እየሳመ ‹‹አሁን ሽልማቴን ለማግኘት እያሰብኩ ነው።››ሲል አከለበት፡፡
‹‹ማለት የምን ሽልማት?፡፡››
‹‹ስለ ሁለተኛ ዙር ምን ትያለሽ?›› አላት፡፡
‹እንደ መጀመሪያው ዙር ጥሩ ከሆነ..ደስ ይለኛል›› አለችው፡፡ያልጠበቀውና …ደስ ያሰኘው መልስ ነበር፡፡
‹‹እንደውም ከመጀመሪያውም የተሻለ እንዲሆን የተቻለኝን አደርጋለሁ››አላትና ድፍረት የታከለበት ቃል ገባላት፡፡ከዛ በትዕግስት እየጸለየ ወገቧን ይዞ ወደ ስር ጎተታት።ትኩር ብላ ተመለከተችው፣ በደረቷ አስተኛትና ከላዮ ወጣ…አይኖቾ ፈጠጡ..የእውነትም ቃል እንደገባላት በጣም ጣፋጭና ማራኪ ነበር፡፡ግን በጣም እያመማት ነው…እንደውም የተላጠችና የደማች እየመሰላት ነው፡፡እንደዛም ሆኖ አቁም በቃኝ ልትለው ፍላጎት አልነበራትም፡፡አንባዋ ሲንጠባጠብና አንሶላውን ሲያረጥበው ተመለከታት…እሱም ላብ በግንባሩ ችፍ እያለ‹‹አሁን ለቅሷ ጥሩ ምልክት ነው ወይስ መጥፎ?›› ብሎ ጠየቃት ፡፡
በተሰባበረ ድምፅ ‹‹ጥሩ ነው።በጣም ጥሩ…ደስ ብሎኝ ነው ።››አለችው፡፡
ድምፁ ፍፅም እርካታንና ደስታን የሚያንፀባርቅ ነው፡፡ ‹‹ደስ ስላለሽ ደስ ብሎኛል››አላት
፡፡ጠንከር ባለ መልኩ ከሱ ስር ተጣበቀች።ግፊቶች እየጠነከሩ እና ፈጣን እና የበለጠ የማያቋርጥ ሆነዋል። የደስታው ፍንዳታ እንደድንገተኛ ማዕበል በውስጧ ሲስገመገም ይሰማታል…አጓራች ። በመጨረሻው የእርካታ ጫፍ ላይ ስትወጣ ከፍተኛ ህመም እና በቃላት ሊገለጽ የማይችል ደስታ አጥለቀለቃት፡፡ ሁለቱም ሻወር ገብተው ታጥበው ወደአልጋቸው ከተመለሱ በኃላ
‹‹ታዲያ፣ አሁን ከአስር ውጤት ለመስጠት ዝግጁ ነሽ?›› ሲል ጠየቃት።
ልታፈር ይገባ ነበር፣ ነገር ግን በጣም ደንዝዛለች፤ በጣም ረክታለች፣ ስለ ራሷ በጣም ጥሩ ነገር ተሰምቷት፡፡ ‹‹ከዘጠኝ በታች የምትሰጪኝ ከሆነ ማወቅ አልፈልግም››አላት፡፡
በሳቅ እየተንከተከተች ‹‹ከአሥሩ አሥር እንዳገኘህ አስባለሁ››አለችው፡፡
በደስታ ሳቀና ‹‹ግን አሳመምኩሽ እንዴ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ፣ አላመመኝም››አለች ፡፡በራሷ መልስ እፍረት ተሰማት፡፡ከዚህ ሰው ጋር ምንም አይነት ቅርርብ ውስጥ ልትወድቅ አትችልም። ያደረጉት ነገር ከአንድ የደስታ ምሽት ያለፈ ትርጉም ሊኖረው አይችልም። ያንን አውቃለች። እሱ ከእርሷ ደረጃ በጣም ሩቅ ነበር ፣
እጁን ዘርግቶ በመደገፍ ጣቶቹን በጣቶቿ ውስጥ አቆላለፈ። ወደጆሮዋ ተጠጋና በሹክሹክታ ‹‹በጣም ጣፋጭ ነሽ የእኔ ቆንጆ››አላት
…‹‹ጨካኝ ድምፁ ከማንኛውም መድሃኒት የበለጠ ሱስ ያሲይዛል።››ስትል በውስጦ አሰበች፡፡
እንቅልፍና ድካም ተጋግዘው አዛሏት ፡፡ እግሮቿ ማራቶን እንደሮጠ ሰው ይመስል በጣም ተዝለፍልፈዋል። እጇን ዘረጋች። አይኖቾን ጨፈነች…ግን ከመተኛት ይልቅ በሀሳብ ተዋጠች፡፡
ዘሚካኤል ሁል ጊዜ ከወሲብ በኋላ መተቃቀፍን አይፈልግም ነበር፡፡ይህ የተለመደና የቆየ ልማዱ ነው…ከወሲብ በኃላ የአልጋውን ጠርዝ ይዞና ፊቱን በሴቲቱ በተቃራኒው ካልዞረ ምቾትም አይሰማውም.. እንቅልፍም አይወስደውም ነበር፡፡ ታዲያ ለምን አሁን እሷን ሰውነቱ ላይ ለጥፎ ክንዱ ላይ አስተኝቶ ትንፋሿን እየማገ ለመተኛት ፈቀደ…. ? ለዛውም ደስ እያለው..ላዛውም ምቾት እየተሰማው..?‹‹ይህቺ ልጅማ የሆነ እስከአሁን በውል ያልተገነዘብኩት አንድ የተለየ ነገር አላት››ሲል አሰበ፡፡
እሷም በተመሳሳይ ሁኔታ ስለሰሩት ፍቅራና እያሰላሰለች ነበር፡፡ ከስድስት ዓመታት በፊት ተመሳሳይ ገጠመኝ አጋጥሟት ነበር፣ ያ ግን ደስ የማይል ነገር ነበር።በወቅቱ ያንን ወሲብ የፈጸመችው ምንም አይነት ፍላጎት ሳይኖራት ነበር፡፡እርግጥ ፍቅረኛዋን አምርራ ትወደው ነበር….እና እሱ በወቅቱ ክፍኛ ፈልጎ ስለነበር እሱን ላለማስቀየምና በዛ ተማሮ እንዳይተዋት በመፍራት ፈቀደችለት….አደረጉ …ለእሷ የተረፋት ልብ የሚሰነጥቅ ህመምና አንሶላ ሚያቀልም ደም ብቻ ነበር፡፡ እና እንደዛም ሆኖ እሱን ማጣቷ አልቀረም ነበር፡፡እና ከሁለት ያጣች ሆነች፡፡ከዛም አልፎ አረገዘች፡፡እና በእንደዛ አይነት የተደራረበ ምክንያት ወሲብ የሚባል ነገር በሀሳብ ደረጃ እንኳን ወደአእምሮዋ ብልጭ እንዳይል መታገል ጀመረች፡፡እናም ለስድስት አመት እራሷን ማቀብ ተሳካላት፡፡ ለምን ሌላ እሷ ለረጅም ጊዜ ያለ ወሲብ ትሄዳለች? ግን እሷ ጋር መተኛት ለእሱ አስፈላጊ የሆነው ለምንድነው? ኃላፊነት የሚሰማውስ ለምንድን ነው? ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት እየባተተች እንቅልፍ ይዞት ጥርግ አለ….እሱም ወዲያው እሷን ተከትሎ ተኛ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 ለመግባት #63 ሰው ብቻ ይቀራል በነገራችን ላይ በአንድ ቀን ሊሞላ የሚችል ነገር ነበር ግን አልሆነም በተቻላቹ አቅም subscriber እያደረጋቹ ቤተሰቦች
ለሁሉም በቅድሚያ አመሰግናለሁ👍
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይ በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ ጠረን ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡
…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።
ዛሬ አዲስአለም እና ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡
አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡
ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡
መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/
አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/
ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል
ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››
የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››
ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው መጡበት፡፡
ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››
‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››
‹‹እሺ አናግረኝ…
‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››
‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››
‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››
‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡
‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››
‹‹ጓደኛሽ?››
‹‹ማ ፀዲ››
‹‹አዎ…››
‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››
‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››
‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››
‹‹ወደእናቷ ጋር፡››
‹‹በይ እንቺ ደውይላት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይ በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ ጠረን ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡
…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።
ዛሬ አዲስአለም እና ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡
አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡
ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡
መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/
አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/
ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል
ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››
የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››
ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው መጡበት፡፡
ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››
‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››
‹‹እሺ አናግረኝ…
‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››
‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››
‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››
‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡
‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››
‹‹ጓደኛሽ?››
‹‹ማ ፀዲ››
‹‹አዎ…››
‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››
‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››
‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››
‹‹ወደእናቷ ጋር፡››
‹‹በይ እንቺ ደውይላት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››
‹‹ሚሴጅ ላከችልኝ..አንብቤ ግራ በመጋባት ስደውልላት ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እስኪ አሁን ከፍታው ከሆነ ሞክሪ›
ተቀበለችውና በቃሏ ምታውቀውን ቁጥር ፀፈችና ደወለች….መልሳ ደግማ ደወለች….‹‹አይሰራም›› ብላ መለሰችለትና‹‹ምን አድርገሀት ነው ..?እስኪ ንገረኝ››ብላ በእርጋታ ጠየቀችው፡፡
‹‹ደስ የሚል ጣፋጭ ለሊት ነበር ያሳለፍነው…ሁለታችን በደስታ ሰክረን ነበር…ከእኔም ሆነ ከእሷ ምንም የጎደለ ነገር አልነበረም…ጥዋት አይኔን ስገልጥ ከጎኔ የለችም..ክፍል ውስጥ ብፈልጋት ላገኛት አልቻልኩም..ከዛ ሳይ ብጣሽ ወረቀት ጥላልኝ ሄዳለች ፡፡
አዲስአለም በሳቅ ተንከተከተች
‹‹እኔ በንዴት ጦፌለሁ አንቺ ትስቂያለሽ?››
‹‹ጓደኛዬ እኮ ነች የምታስቀኝ..እሷ እንዲህ ነች….ከአንተ እኮ አይደለም የሸሸችው››
‹‹እና ከማን ነው?››
‹‹ ከፍቅር››
‹‹እንዴ ከፍቅር ይሸሻል እንዴ?››
‹‹አዎ እሷ እንደዚህ ነች…እየወደደችህ ይመስለኛል…እና አንተ ጥለሀት ሄደህ እንዳትጎዳ ስለምትፈራ ቀድማ ጥላህ እየሄደች ነው…››
‹‹አይ እንደዛማ እንድታደርግ አልፈቅድላትም..ከእኔ ሸሽታ አታመልጥም››
‹‹እንዴ…ያን ያህል አምርረሀል እንዴ?››
‹‹አዎ …የተለየ ስሜት እንዲሰማኝ አድርጋኛለች…እንዲሁ አንደቀልድ ልለቃት አልፈልግም…››
‹‹ቀጣይ እርምጀ ከመውሰድህ በፊት ተረጋግተህ አስብበት…እንድትጎዳት ፈፅሞ አልፈልግም…የማትዘልቅበት ከሆነ አሁን በሰጠችህ የማርያም መንገድ ሾልክ ከህይወቷ ውጣ››
‹‹አይ አልወጣም…ይሄውልሽ ዛሬ ወደዱባይ በረራ አለብኝ..አሁኑኑ ወደ አዲስአበባ ሄጄ መዘጋጀት አለብኝ..ከሳምንት በኃላ ተመልሼ ስመጣ ካቆምንበት እቀጥላለን በያት..››
መኪናውን ሞተር አስነሳና ወደአስፓልቱ መልሶ አስገብቷ ወደኃላ ዞረና እቤቷ በራፍ ላይ ወስዶ አወረዳት..ሚካኤል ቅድም በተገተረበት ቆሞ በስጋት ሲጠብቃቸው ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች ቢያንስ 1--2 ሰው በአንድ ፖስት 500 subscriber ናፈቀን እኮ😞😞
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹እስኪ አሁን ከፍታው ከሆነ ሞክሪ›
ተቀበለችውና በቃሏ ምታውቀውን ቁጥር ፀፈችና ደወለች….መልሳ ደግማ ደወለች….‹‹አይሰራም›› ብላ መለሰችለትና‹‹ምን አድርገሀት ነው ..?እስኪ ንገረኝ››ብላ በእርጋታ ጠየቀችው፡፡
‹‹ደስ የሚል ጣፋጭ ለሊት ነበር ያሳለፍነው…ሁለታችን በደስታ ሰክረን ነበር…ከእኔም ሆነ ከእሷ ምንም የጎደለ ነገር አልነበረም…ጥዋት አይኔን ስገልጥ ከጎኔ የለችም..ክፍል ውስጥ ብፈልጋት ላገኛት አልቻልኩም..ከዛ ሳይ ብጣሽ ወረቀት ጥላልኝ ሄዳለች ፡፡
አዲስአለም በሳቅ ተንከተከተች
‹‹እኔ በንዴት ጦፌለሁ አንቺ ትስቂያለሽ?››
‹‹ጓደኛዬ እኮ ነች የምታስቀኝ..እሷ እንዲህ ነች….ከአንተ እኮ አይደለም የሸሸችው››
‹‹እና ከማን ነው?››
‹‹ ከፍቅር››
‹‹እንዴ ከፍቅር ይሸሻል እንዴ?››
‹‹አዎ እሷ እንደዚህ ነች…እየወደደችህ ይመስለኛል…እና አንተ ጥለሀት ሄደህ እንዳትጎዳ ስለምትፈራ ቀድማ ጥላህ እየሄደች ነው…››
‹‹አይ እንደዛማ እንድታደርግ አልፈቅድላትም..ከእኔ ሸሽታ አታመልጥም››
‹‹እንዴ…ያን ያህል አምርረሀል እንዴ?››
‹‹አዎ …የተለየ ስሜት እንዲሰማኝ አድርጋኛለች…እንዲሁ አንደቀልድ ልለቃት አልፈልግም…››
‹‹ቀጣይ እርምጀ ከመውሰድህ በፊት ተረጋግተህ አስብበት…እንድትጎዳት ፈፅሞ አልፈልግም…የማትዘልቅበት ከሆነ አሁን በሰጠችህ የማርያም መንገድ ሾልክ ከህይወቷ ውጣ››
‹‹አይ አልወጣም…ይሄውልሽ ዛሬ ወደዱባይ በረራ አለብኝ..አሁኑኑ ወደ አዲስአበባ ሄጄ መዘጋጀት አለብኝ..ከሳምንት በኃላ ተመልሼ ስመጣ ካቆምንበት እቀጥላለን በያት..››
መኪናውን ሞተር አስነሳና ወደአስፓልቱ መልሶ አስገብቷ ወደኃላ ዞረና እቤቷ በራፍ ላይ ወስዶ አወረዳት..ሚካኤል ቅድም በተገተረበት ቆሞ በስጋት ሲጠብቃቸው ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች ቢያንስ 1--2 ሰው በአንድ ፖስት 500 subscriber ናፈቀን እኮ😞😞
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ሚካኤል ከኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች ከፍተኛ ኃላፊ ጋር ሚስጥራዊ ስብስባ እያደረገ ነው፡፡እኚን ባለስልጣን ለማግኘትና ለማናገር በጣም ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፏል …በጣም ብዙ ገንዘብም ከስክሷል፡፡
‹‹እሺ አቶ ሚካኤል እንዳገኝህ ያሳመነን ወዳጄ ትልቅ ባለውለታዬ ነው ..ምን እንዳደርግልህ ነው የምትፈልገው?፡፡››ሲል ቦርጫቸውን እሻሹ ጠየቁት፡፡
‹‹ያው ጫፉን ያውቁታል ስለአባቴ ጉዳይ ነው››
‹‹እሱን ሰምቼለው…አባትህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሰው ነው፡፡ምን እንድረዳህ እንደፈለክም ያልገባኝ ለዛ ነው፡፡ታውቃለህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ፍርደኛ ቀጥታ ፋይሉ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ጋር ነው ሚላከው..እሳቸው ሲፈርሙበት የሞት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል…እስከዛው በእስር ይቆያል…ማንም ሰው ምንም ማድረግ አይችልም፡፡››
‹‹አውቃለው…..የእኔ ፍላጎት የሞት ፍርድ ተፈፃሚ እስኪሆንበት ያለው የማረሚያ ቤቱ አያያዝ እንዲሻሻልለት ለመጠየቅ ነው፡፡››
‹‹አዎ አንተን ለማግኘት ከመምጣቴ በፊት ስለአባትህ አጠቃላይ ሁኔታ በመጠኑ ለማጣራት ሞክሬ ነበር፡፡አሁን የታሰረው ጥብቅ በሆነ ጥበቃ ለብቻው መሆኑን ገልፀውልኛል፡፡››አሉን ፊትለፊታቸው የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ አንስተው ተጎነጩና መልሰው አስቀመጡት፡፡
ሚካኤልም ‹‹አዎ ያስጨነቀኝ እኮ ያ ነው፡፡››ሲል መለሰላቸው፡፡
‹‹ያ ለምን እንደሆነ መቼስ ታውቃለህ፡፡አባትህ ከሌሎች በእስር ቤት ካሉ ታራሚሆች ጋር በማሰር ከማረሚያ ቤቱ ለማምለጥ ሞክሮ አንድ የፖሊስ አባልና ሁለት እስረኛ ሞተዋል፡፡የዛ ኦፕሬሽን ዋናው ማስተር ማይንድ እና መሪ ደግሞ አባትህ ነበር…ያ ውሳኔ የተወሰነበት ከዛ ክስተት በኋላ ነው፡፡ለፖሊስ መገደል ምክንያት መሆን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መገመት አይከብድህም››
‹‹አዎ አውቃለው…ግን እኮ በጣም ተቀጣ..እዛ ጨለማ ክፍል በሰንሰለት ተጠፍሮ መኖር ከጀመረ ስድስት ወር አለፈው፡፡እሺ ብቻውን ይታሰር….ቢያንስ ከጨለማ ክፍል የሚወጣበትና ከሰንሰለት እስርም የሚገላገልበት እድል ቢኖር፡፡ዋናው ከሰው እንዳይቀላቀልና ተመሳሳይ አይነት የማምለጥ ሙከራ እንዳይሞክር አይደል››ሲል በንግግሩ ቃናም በአይኖቹም ተማፀናቸው፡፡
‹‹ይመስለኛል ..ያም ብቻ አይደለም..በእሱ ምክንያት የሞተው ፖሊስ በወህኒ ቤት ውስጥ በፖሊስችም ሆነ በእስረኞች በጣም ተወዳጅ ስለነበረ….በጓደኞቹ ዘንድ ከፍተኛ ብስጭት ፈጥሯል….እና አንድም በጣም እንዲቀጣ ይፈልጋሉ በሌላ ጎኑም በተግባሩ በተበሳጩ ሰዎች ጥቃት እንዳይደርስበትም ስጋት ስላለ መጠበቅ ይፈልጋሉ፡፡››
‹‹‹አውቃለሁ…ያ ጉዳይ በመፈፀሙ እኔም ከፍተኛ ልብ ስብራት ደርሶብኛል ፣ የሞች ፖሊስ ቤተሰቦች አግኝቼ ለማነጋገር ሞክሬለው፡፡ባለቤቱንና አንድ ልጁን ወዲው ነበር ያገኘዋቸው….እና ምንም እንኳን እሱን መልሼ ላመጣላቸው ባልችልም በኑሮ ግን እንዳይቸገሩ የተቻለኝን እያደረኩ ነው፡፡ለሚስቱ ስራ እንድታገኝ አድርጌለው….የልጁንም ትምህርት ቤት ክፍያ እና አንዳንድ ወጪዎች እየከፈልኩ ነው….ምንም ሆነ ምንም ወደፊትም ያንን ማድረጌን አላቋርጥም፣እባኮት እርሶ በተቻሎት መጠን ይርዱኝ…ምንም አይነት ቤተሰብ እንዳይጠይቀውም ስለተከለከለ እኔ እንኳን ካየሁት ስድስት ወር አልፎኛል…››
‹‹በእውነት እያደረከው ስላለ ነገር ምስጋና ይገባሀል..ትልቅ ሰው ነህ!!እንግዲህ እንዲህ እናድርግ….አንድ አስር ቀን ስጠኝ እና ሁኔታውን በተሻለ ሁኔታ ላጥና..ከዛ ሌሎች ጓደኞቼንም ቢሆን አስቸግሬ ማድረግ የምችለውን ነገር ላስብበትና መልሰን እናውራበት››
‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው…..ምን አልባት ጓደኞቾትን ሲያስቸግሩ የሚያስፈልግ ነገር ካለ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አሟላለሁ…፡፡››ሲል ቃል ገባ፡፡
‹‹ችግር የለም… የሚስፈልግ ነገር ካለ አሳውቅሀለው….እነደነገርኩህ አንተን እንድረዳህ የጠየቀኝ ሰው በጣም ወዳጄና ባለውለታዬ ነው…..እና በእኔ አቅም ማድረግ የምችለውን ነገር ሁሉ እንደማደርግና የአባትህን በእስር ቤት ውስጥ ያለውን አያያዝ ለማሻሻል ጥረት እንደማደረግ ልገልጽልህ አፈልጋለው…በተለይ አባትህን የመጠየቅ መብትህን መልሰህ እንድታገኝ ማድረግ ምችል ይመስለኛል፡፡››
‹‹አመሰግናለው..ስልኮትን በጉጉት ጠብቃለው፡፡›› በዛው ተለያዩ
////
ፀአዳ በአራተኛው ቀን ስሜቷን አብርዳ….መረበሿን አረጋግታ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ከዶዶላ ተመልሳ አዳማ እስክትገባ ስልኳን አልከፈተችም ነበር፡፡ቤቷ ደርሳ አረፍ እንዳለች ከፈተችና ለአዲስ አለም ደወለችላት፡፡
አዲስአለም ከሰላምታ ሳይሆን ከስድብ ነው የጀመረችው‹‹አንቺ ቅሌታም…..ጤነኛ ነሽ ግን?››
‹‹ቀስ …ይሄ ሁሉ ቁጣ ናፍቆት ነው ወይስ ሌላ ምክያት አለው?፡፡››
በስድቧ ገፋችበት ‹‹ወሬኛ ነሽ እሺ…..ለመሆኑ አሁን የት ነሽ?››
‹‹ቤቴ ነኛ››
‹‹ማለት እዚህ አዳማ?››
‹‹አዎ..ምነው ሌላ ቦታ ቤት አለኝ እንዴ?››
‹‹እኔ ምን አውቅልሻለው….ግን ሳስበው በቅርብ አዲስአበባ ላይ ቤት የሚኖርሽ ይመስለኛል….በቃ ጠብቂኝ አሁኑኑ መጣሁ…፡፡››
‹‹ኸረ እኔ ራሴ መጣለሁ…፡፡››
‹‹መጣው እኮ አልኩሽ፡፡››ስልኩን ጠረቀመችባት፡፡
‹‹ዛሬ ልትደበድበኝ ሁሉ ትችላለች››ስትል አሰበችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ማስተካከል ጀመረች ..ተዘግቶ ስለከረመ እምክ እምክ ይላል…መስኮቱን ከፋፈተች…ሰንደል ለኮሶችና በየኮርነሩ ላይ ሰካካች… ቡና ለማፍላት ሲኔ ደረደረች፣ከሰል በማቀጣጠል ላይ እያለች አዲስ አለም መጣች፡፡
ጠየቀቻት ካሰበችው ጊዜ በጣም ፈጥና በመምጠቷ ተገርማ‹‹እንዴ ..!!ስትደውይልኝ መንገድ ላይ ነበርሽ እንዴ?››ስትል ….፡፡
ልትስማት ስትጠጋት ወደኃ ሸሸቻትና ገፍትራት ወደቤት ገባች….ፀአዳማ እያቀጣጠለች የነበረውን ከሰል ትታ ከኃላ ተከተለቻት፡፡
‹‹ምስር የታለች?››
‹‹ጎረቤት ልትጫወት ሄዳለች››
‹‹ቆይ አንቺ ግን ያምሻል..?እንዴት አንድ ነር ሳትነግሪኝ ብን ብለሽ ትሔጃለሽ…እሺ መሄዱንስ ሂጂ እንዴትሰ ስልክሽን ትዘጊያለሽ?››
‹‹ስልኬ እኮ ተበላቶብኝ ነው››
‹‹አረ ባክሽ..አሁን እኔን የምትሸውጂኝ ይመስልሻል?››
‹‹‹እሺ በቃ ማንንም ለማውራት ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም…በፀጥታ ማሰብ ነበር የፈለኩት..በዛ ላይ አንቺ የሰርግና የመልስ ግርግር ላይ ስለሆንሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም››
‹‹ወይ ረበሺኝ እኮ..እኔን ብቻ ሳይሆን ባሌንም ጭምር ነው በደንብ የረበሺን፡፡››
‹‹እንግዲህ አዝናለው…..በጣም ይቅርታ›
‹‹ደግሞ ሰውዬሽ..አብዶልሻል….››
‹‹የቱ ሰውዬ?››ግራ በመጋባት ጠየቀች፡፡
‹‹ስንት ሰውዬ ነው ያለሽ…?ዘሚካኤል ነዋ..ከደበቅሺበት ውለጂያት ብሎ ሊያንቀኝ››
‹‹እንዴ ደወለልሽ እንዴ?››
ምን ይደውልልኛል…በዛን ቀን ልክ ያንቺ መልእክት ደርሶኝ እሱን ከሚካኤል ጋር አንብበን እየተገረምን ሳለ ቤት ድረስ መኪናውን እያከነፈ መጣና ሰፈሩን በመኪናው ክላክስ አደበላለቀው…ምን ሆኖ ነው ብዬ ስወጣ መኪና ውስጥ አስገባኝና ከሰፈር ይዞኝ ሄደ….››ብላ የዛን ቀን የሆነውን በዝርዝር ተረከችላት፡፡›
ፀአዳ በሰማችው ነገር በጣም ተገረመች‹‹ፈፅሞ እንደዛ ያደርጋል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር…ግፋ ቢል ደውሎ የሆነ ነገር ይልሻል ብዬ ነው ያሰብኩት፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?ልጁ እኮ ጨርቁን ጥሎልሻል››
‹‹ማለት?››
‹‹አፍቅሯሻል እያልኩሽ ነው››
‹‹እኔ ፍቅር አልፈልግም››
‹‹እና ወሲብ ነው ምትፈልጊው?
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ሚካኤል ከኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች ከፍተኛ ኃላፊ ጋር ሚስጥራዊ ስብስባ እያደረገ ነው፡፡እኚን ባለስልጣን ለማግኘትና ለማናገር በጣም ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፏል …በጣም ብዙ ገንዘብም ከስክሷል፡፡
‹‹እሺ አቶ ሚካኤል እንዳገኝህ ያሳመነን ወዳጄ ትልቅ ባለውለታዬ ነው ..ምን እንዳደርግልህ ነው የምትፈልገው?፡፡››ሲል ቦርጫቸውን እሻሹ ጠየቁት፡፡
‹‹ያው ጫፉን ያውቁታል ስለአባቴ ጉዳይ ነው››
‹‹እሱን ሰምቼለው…አባትህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሰው ነው፡፡ምን እንድረዳህ እንደፈለክም ያልገባኝ ለዛ ነው፡፡ታውቃለህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ፍርደኛ ቀጥታ ፋይሉ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ጋር ነው ሚላከው..እሳቸው ሲፈርሙበት የሞት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል…እስከዛው በእስር ይቆያል…ማንም ሰው ምንም ማድረግ አይችልም፡፡››
‹‹አውቃለው…..የእኔ ፍላጎት የሞት ፍርድ ተፈፃሚ እስኪሆንበት ያለው የማረሚያ ቤቱ አያያዝ እንዲሻሻልለት ለመጠየቅ ነው፡፡››
‹‹አዎ አንተን ለማግኘት ከመምጣቴ በፊት ስለአባትህ አጠቃላይ ሁኔታ በመጠኑ ለማጣራት ሞክሬ ነበር፡፡አሁን የታሰረው ጥብቅ በሆነ ጥበቃ ለብቻው መሆኑን ገልፀውልኛል፡፡››አሉን ፊትለፊታቸው የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ አንስተው ተጎነጩና መልሰው አስቀመጡት፡፡
ሚካኤልም ‹‹አዎ ያስጨነቀኝ እኮ ያ ነው፡፡››ሲል መለሰላቸው፡፡
‹‹ያ ለምን እንደሆነ መቼስ ታውቃለህ፡፡አባትህ ከሌሎች በእስር ቤት ካሉ ታራሚሆች ጋር በማሰር ከማረሚያ ቤቱ ለማምለጥ ሞክሮ አንድ የፖሊስ አባልና ሁለት እስረኛ ሞተዋል፡፡የዛ ኦፕሬሽን ዋናው ማስተር ማይንድ እና መሪ ደግሞ አባትህ ነበር…ያ ውሳኔ የተወሰነበት ከዛ ክስተት በኋላ ነው፡፡ለፖሊስ መገደል ምክንያት መሆን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መገመት አይከብድህም››
‹‹አዎ አውቃለው…ግን እኮ በጣም ተቀጣ..እዛ ጨለማ ክፍል በሰንሰለት ተጠፍሮ መኖር ከጀመረ ስድስት ወር አለፈው፡፡እሺ ብቻውን ይታሰር….ቢያንስ ከጨለማ ክፍል የሚወጣበትና ከሰንሰለት እስርም የሚገላገልበት እድል ቢኖር፡፡ዋናው ከሰው እንዳይቀላቀልና ተመሳሳይ አይነት የማምለጥ ሙከራ እንዳይሞክር አይደል››ሲል በንግግሩ ቃናም በአይኖቹም ተማፀናቸው፡፡
‹‹ይመስለኛል ..ያም ብቻ አይደለም..በእሱ ምክንያት የሞተው ፖሊስ በወህኒ ቤት ውስጥ በፖሊስችም ሆነ በእስረኞች በጣም ተወዳጅ ስለነበረ….በጓደኞቹ ዘንድ ከፍተኛ ብስጭት ፈጥሯል….እና አንድም በጣም እንዲቀጣ ይፈልጋሉ በሌላ ጎኑም በተግባሩ በተበሳጩ ሰዎች ጥቃት እንዳይደርስበትም ስጋት ስላለ መጠበቅ ይፈልጋሉ፡፡››
‹‹‹አውቃለሁ…ያ ጉዳይ በመፈፀሙ እኔም ከፍተኛ ልብ ስብራት ደርሶብኛል ፣ የሞች ፖሊስ ቤተሰቦች አግኝቼ ለማነጋገር ሞክሬለው፡፡ባለቤቱንና አንድ ልጁን ወዲው ነበር ያገኘዋቸው….እና ምንም እንኳን እሱን መልሼ ላመጣላቸው ባልችልም በኑሮ ግን እንዳይቸገሩ የተቻለኝን እያደረኩ ነው፡፡ለሚስቱ ስራ እንድታገኝ አድርጌለው….የልጁንም ትምህርት ቤት ክፍያ እና አንዳንድ ወጪዎች እየከፈልኩ ነው….ምንም ሆነ ምንም ወደፊትም ያንን ማድረጌን አላቋርጥም፣እባኮት እርሶ በተቻሎት መጠን ይርዱኝ…ምንም አይነት ቤተሰብ እንዳይጠይቀውም ስለተከለከለ እኔ እንኳን ካየሁት ስድስት ወር አልፎኛል…››
‹‹በእውነት እያደረከው ስላለ ነገር ምስጋና ይገባሀል..ትልቅ ሰው ነህ!!እንግዲህ እንዲህ እናድርግ….አንድ አስር ቀን ስጠኝ እና ሁኔታውን በተሻለ ሁኔታ ላጥና..ከዛ ሌሎች ጓደኞቼንም ቢሆን አስቸግሬ ማድረግ የምችለውን ነገር ላስብበትና መልሰን እናውራበት››
‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው…..ምን አልባት ጓደኞቾትን ሲያስቸግሩ የሚያስፈልግ ነገር ካለ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አሟላለሁ…፡፡››ሲል ቃል ገባ፡፡
‹‹ችግር የለም… የሚስፈልግ ነገር ካለ አሳውቅሀለው….እነደነገርኩህ አንተን እንድረዳህ የጠየቀኝ ሰው በጣም ወዳጄና ባለውለታዬ ነው…..እና በእኔ አቅም ማድረግ የምችለውን ነገር ሁሉ እንደማደርግና የአባትህን በእስር ቤት ውስጥ ያለውን አያያዝ ለማሻሻል ጥረት እንደማደረግ ልገልጽልህ አፈልጋለው…በተለይ አባትህን የመጠየቅ መብትህን መልሰህ እንድታገኝ ማድረግ ምችል ይመስለኛል፡፡››
‹‹አመሰግናለው..ስልኮትን በጉጉት ጠብቃለው፡፡›› በዛው ተለያዩ
////
ፀአዳ በአራተኛው ቀን ስሜቷን አብርዳ….መረበሿን አረጋግታ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ከዶዶላ ተመልሳ አዳማ እስክትገባ ስልኳን አልከፈተችም ነበር፡፡ቤቷ ደርሳ አረፍ እንዳለች ከፈተችና ለአዲስ አለም ደወለችላት፡፡
አዲስአለም ከሰላምታ ሳይሆን ከስድብ ነው የጀመረችው‹‹አንቺ ቅሌታም…..ጤነኛ ነሽ ግን?››
‹‹ቀስ …ይሄ ሁሉ ቁጣ ናፍቆት ነው ወይስ ሌላ ምክያት አለው?፡፡››
በስድቧ ገፋችበት ‹‹ወሬኛ ነሽ እሺ…..ለመሆኑ አሁን የት ነሽ?››
‹‹ቤቴ ነኛ››
‹‹ማለት እዚህ አዳማ?››
‹‹አዎ..ምነው ሌላ ቦታ ቤት አለኝ እንዴ?››
‹‹እኔ ምን አውቅልሻለው….ግን ሳስበው በቅርብ አዲስአበባ ላይ ቤት የሚኖርሽ ይመስለኛል….በቃ ጠብቂኝ አሁኑኑ መጣሁ…፡፡››
‹‹ኸረ እኔ ራሴ መጣለሁ…፡፡››
‹‹መጣው እኮ አልኩሽ፡፡››ስልኩን ጠረቀመችባት፡፡
‹‹ዛሬ ልትደበድበኝ ሁሉ ትችላለች››ስትል አሰበችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ማስተካከል ጀመረች ..ተዘግቶ ስለከረመ እምክ እምክ ይላል…መስኮቱን ከፋፈተች…ሰንደል ለኮሶችና በየኮርነሩ ላይ ሰካካች… ቡና ለማፍላት ሲኔ ደረደረች፣ከሰል በማቀጣጠል ላይ እያለች አዲስ አለም መጣች፡፡
ጠየቀቻት ካሰበችው ጊዜ በጣም ፈጥና በመምጠቷ ተገርማ‹‹እንዴ ..!!ስትደውይልኝ መንገድ ላይ ነበርሽ እንዴ?››ስትል ….፡፡
ልትስማት ስትጠጋት ወደኃ ሸሸቻትና ገፍትራት ወደቤት ገባች….ፀአዳማ እያቀጣጠለች የነበረውን ከሰል ትታ ከኃላ ተከተለቻት፡፡
‹‹ምስር የታለች?››
‹‹ጎረቤት ልትጫወት ሄዳለች››
‹‹ቆይ አንቺ ግን ያምሻል..?እንዴት አንድ ነር ሳትነግሪኝ ብን ብለሽ ትሔጃለሽ…እሺ መሄዱንስ ሂጂ እንዴትሰ ስልክሽን ትዘጊያለሽ?››
‹‹ስልኬ እኮ ተበላቶብኝ ነው››
‹‹አረ ባክሽ..አሁን እኔን የምትሸውጂኝ ይመስልሻል?››
‹‹‹እሺ በቃ ማንንም ለማውራት ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም…በፀጥታ ማሰብ ነበር የፈለኩት..በዛ ላይ አንቺ የሰርግና የመልስ ግርግር ላይ ስለሆንሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም››
‹‹ወይ ረበሺኝ እኮ..እኔን ብቻ ሳይሆን ባሌንም ጭምር ነው በደንብ የረበሺን፡፡››
‹‹እንግዲህ አዝናለው…..በጣም ይቅርታ›
‹‹ደግሞ ሰውዬሽ..አብዶልሻል….››
‹‹የቱ ሰውዬ?››ግራ በመጋባት ጠየቀች፡፡
‹‹ስንት ሰውዬ ነው ያለሽ…?ዘሚካኤል ነዋ..ከደበቅሺበት ውለጂያት ብሎ ሊያንቀኝ››
‹‹እንዴ ደወለልሽ እንዴ?››
ምን ይደውልልኛል…በዛን ቀን ልክ ያንቺ መልእክት ደርሶኝ እሱን ከሚካኤል ጋር አንብበን እየተገረምን ሳለ ቤት ድረስ መኪናውን እያከነፈ መጣና ሰፈሩን በመኪናው ክላክስ አደበላለቀው…ምን ሆኖ ነው ብዬ ስወጣ መኪና ውስጥ አስገባኝና ከሰፈር ይዞኝ ሄደ….››ብላ የዛን ቀን የሆነውን በዝርዝር ተረከችላት፡፡›
ፀአዳ በሰማችው ነገር በጣም ተገረመች‹‹ፈፅሞ እንደዛ ያደርጋል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር…ግፋ ቢል ደውሎ የሆነ ነገር ይልሻል ብዬ ነው ያሰብኩት፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?ልጁ እኮ ጨርቁን ጥሎልሻል››
‹‹ማለት?››
‹‹አፍቅሯሻል እያልኩሽ ነው››
‹‹እኔ ፍቅር አልፈልግም››
‹‹እና ወሲብ ነው ምትፈልጊው?
‹‹እየቀለድኩ አይደለም…በእሱ ሁኔታ አትሸወጂ..ቀድሞኝ ጥሎኝ ዞር ስላላለ ቆጭቷት ነው….ተቀደምኩ ብሎ ነው፡፡››
‹‹በፍፁም ..የእውነት አፍቅሮሻል…..››
‹‹አትመኚው ባክሽ….ለማንኛውም ያከተመለት ነገር ነው…..››
‹‹አይመስለኝም… ሰሞኑን እየከነፈ ይመጣልኛል፡፡››
‹‹መመለሴን እንዳትነግሪው››
‹‹ውይ ብልነግረውም ልክ እንደተመለሰ በሮ ወደእዚህ መምጣቱ አይቀርም…›
‹‹ከየት ነው የሚመለሰው?››
‹‹የዛኑ ቀን ማታ እኮ ወደ ዱባይ ይበር ነበር….ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ነው የሚመለሰው››
‹‹አዎ ስለዱባይ ጉዞ ሲያወራ ሰምቼለው››
‹‹ከዱባይ ሁሉ ሁለት ቀን ደውሎልኝ ስለአንቺ ጠይቆኛል..በአንቺ ሰበብ እኛም ከመቼውም ጊዜ በላይ መቀራረብ ጀምረናል…ምን አልባት በወንድማማቾችን መካከል ያለውን ችግር ቀርፈሽ የምታስማሚያቸው ዋናዋ ሰው አንቺ ትሆኚያለሽ››
‹‹በይ በይ….ቆይ ቡና ላፍላላሽ››
‹‹አልፈልግም ባክሽ…..እኔ አሁን ቡና መች ጠማኝ?››
‹‹እና ወሬ ነው የጠማሽ?››
‹‹አዎ ..ቆይ ግን ..እሱ እንደነገረኝ ከሆን በጣም ልዩ እና ጣፋጭ ለሊት ነበር ያሳለፍነው አለኝ…ምን ለማለት ፈልጎ ነው?››በግማሽ ፈገግታ እና በግማሽ ማሽሟጠጥ መሀከል ሆና ጠየቀቻት፡፡
‹‹እንዴ!!››ፀአዳ ሳቋ አመለጣት፡፡
‹‹እንደዛ አለሽ…?ለምን ታዲያ ማብራሪያውን እሱኑ አትጠይቂውም ነበር?››
‹‹አታሹፊ..እ እስኪ አንቺ ንገሪኝ››በከፍተኛ ፍላጎት እንድትነግራት ገፋፋቻት፡፡
ፀአዳ ሳታስበው ከተቀመጠችበት ተነሳች‹‹የእውነት እኔ በጣም ጣፋጭ ነበር ለማለት አልችልም››
‹‹ምነው አልተመቸሽም ነበር?››
‹‹የዛች ለሊት ከእሱ ጋር የሰራሁት ፍቅር ጣፋጭ ነው ብቻ ተብሎ የሚታለፍ አይደለም….ክንፍ አብቅሎ በአየር ላይ የመንሳፈፍ አይነት ነው….ወይንም በሳተላይት ጨረቃ ላይ ደርሶ እንደመምጣት አይነት ተአምራዊ ልምድ የሚያጎናፅፍ አይነት ነው…ወይንም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ እጅሽን ኪስሽ ውስጥ ከተሸ ወክ እያደረግሽ የመዝናናት አይነት ነው…..ከንፈሩ ወለላ ማር….ትንፋሹ የገነት አየር….ነው፣አይኖቹ አካልሽን ብቻ ሳይሆን ነፍስሽንም ሰርስረው የማየት ብቃት አላቸው፡፡ሲያወራ ቃላቶቹ እራሷቸው ሙዚቃዊ ምት አላቸው፡፡…ምን አለፋሽ….ስክርክር ነበር ያልኩለት››
‹‹ዋው!!ዋው!!.››.አዲስ አለም ከተቀመጠችበት እያጨበጨበች ተነሳች‹‹እንዴ ጓደኛዬ ከመቼ ወዲህ ነው እንዲህ ባለቅኔ የሆንሽው››
‹‹ምን አልባት ፍቅር ባለቅኔ ያደርግ ይሆናላ››
‹‹ታዲያ እኛንስ ምነው ዘለለን…የእኛ ፍቅር ፍቅር አይደለም ማለት ነው፡፡››
‹‹እይ አሱን አላውቅም…እኔ የራሴን ነው የነገርኩሽ››
‹‹እና ከዚህ ሁሉ ተአምራዊ በፍቅርና በፋንታሲ የተሞላ ለሊት በኃላ ብን ብለሽ መጥፋትሽ….ፍፁም ለሰሚው ግራ የሚያጋባ የማይጣጣም ነገር እኮ ነው..ለማንኛውም ተነሽ ምስርና በዛው ይዘናት ወደቤት እንሂድ›
‹‹ቡናውስ?››
‹‹ምን ችግር አለው… እዛው እናስፈላለን…….››
‹‹እንግዲያው ልብሴን ልቀይር መጀመሪያ ግን ስራ ቦታ መድረስ አለብኝ..››ብላ አዲስአለምን በቆመችበት ጥላት ወደመኝታ ክፍሏ ገባች፡፡
‹‹እንደዛ ከሆነ እኔ ቀድሜሽ ወደቤት ልሂድና ቡናውን እያስፈላው እጠብቅሻለው፡፡››አለቻት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 እንደሰማይ ራቀን ቀረብ አድርጉን😃
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹በፍፁም ..የእውነት አፍቅሮሻል…..››
‹‹አትመኚው ባክሽ….ለማንኛውም ያከተመለት ነገር ነው…..››
‹‹አይመስለኝም… ሰሞኑን እየከነፈ ይመጣልኛል፡፡››
‹‹መመለሴን እንዳትነግሪው››
‹‹ውይ ብልነግረውም ልክ እንደተመለሰ በሮ ወደእዚህ መምጣቱ አይቀርም…›
‹‹ከየት ነው የሚመለሰው?››
‹‹የዛኑ ቀን ማታ እኮ ወደ ዱባይ ይበር ነበር….ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ነው የሚመለሰው››
‹‹አዎ ስለዱባይ ጉዞ ሲያወራ ሰምቼለው››
‹‹ከዱባይ ሁሉ ሁለት ቀን ደውሎልኝ ስለአንቺ ጠይቆኛል..በአንቺ ሰበብ እኛም ከመቼውም ጊዜ በላይ መቀራረብ ጀምረናል…ምን አልባት በወንድማማቾችን መካከል ያለውን ችግር ቀርፈሽ የምታስማሚያቸው ዋናዋ ሰው አንቺ ትሆኚያለሽ››
‹‹በይ በይ….ቆይ ቡና ላፍላላሽ››
‹‹አልፈልግም ባክሽ…..እኔ አሁን ቡና መች ጠማኝ?››
‹‹እና ወሬ ነው የጠማሽ?››
‹‹አዎ ..ቆይ ግን ..እሱ እንደነገረኝ ከሆን በጣም ልዩ እና ጣፋጭ ለሊት ነበር ያሳለፍነው አለኝ…ምን ለማለት ፈልጎ ነው?››በግማሽ ፈገግታ እና በግማሽ ማሽሟጠጥ መሀከል ሆና ጠየቀቻት፡፡
‹‹እንዴ!!››ፀአዳ ሳቋ አመለጣት፡፡
‹‹እንደዛ አለሽ…?ለምን ታዲያ ማብራሪያውን እሱኑ አትጠይቂውም ነበር?››
‹‹አታሹፊ..እ እስኪ አንቺ ንገሪኝ››በከፍተኛ ፍላጎት እንድትነግራት ገፋፋቻት፡፡
ፀአዳ ሳታስበው ከተቀመጠችበት ተነሳች‹‹የእውነት እኔ በጣም ጣፋጭ ነበር ለማለት አልችልም››
‹‹ምነው አልተመቸሽም ነበር?››
‹‹የዛች ለሊት ከእሱ ጋር የሰራሁት ፍቅር ጣፋጭ ነው ብቻ ተብሎ የሚታለፍ አይደለም….ክንፍ አብቅሎ በአየር ላይ የመንሳፈፍ አይነት ነው….ወይንም በሳተላይት ጨረቃ ላይ ደርሶ እንደመምጣት አይነት ተአምራዊ ልምድ የሚያጎናፅፍ አይነት ነው…ወይንም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ እጅሽን ኪስሽ ውስጥ ከተሸ ወክ እያደረግሽ የመዝናናት አይነት ነው…..ከንፈሩ ወለላ ማር….ትንፋሹ የገነት አየር….ነው፣አይኖቹ አካልሽን ብቻ ሳይሆን ነፍስሽንም ሰርስረው የማየት ብቃት አላቸው፡፡ሲያወራ ቃላቶቹ እራሷቸው ሙዚቃዊ ምት አላቸው፡፡…ምን አለፋሽ….ስክርክር ነበር ያልኩለት››
‹‹ዋው!!ዋው!!.››.አዲስ አለም ከተቀመጠችበት እያጨበጨበች ተነሳች‹‹እንዴ ጓደኛዬ ከመቼ ወዲህ ነው እንዲህ ባለቅኔ የሆንሽው››
‹‹ምን አልባት ፍቅር ባለቅኔ ያደርግ ይሆናላ››
‹‹ታዲያ እኛንስ ምነው ዘለለን…የእኛ ፍቅር ፍቅር አይደለም ማለት ነው፡፡››
‹‹እይ አሱን አላውቅም…እኔ የራሴን ነው የነገርኩሽ››
‹‹እና ከዚህ ሁሉ ተአምራዊ በፍቅርና በፋንታሲ የተሞላ ለሊት በኃላ ብን ብለሽ መጥፋትሽ….ፍፁም ለሰሚው ግራ የሚያጋባ የማይጣጣም ነገር እኮ ነው..ለማንኛውም ተነሽ ምስርና በዛው ይዘናት ወደቤት እንሂድ›
‹‹ቡናውስ?››
‹‹ምን ችግር አለው… እዛው እናስፈላለን…….››
‹‹እንግዲያው ልብሴን ልቀይር መጀመሪያ ግን ስራ ቦታ መድረስ አለብኝ..››ብላ አዲስአለምን በቆመችበት ጥላት ወደመኝታ ክፍሏ ገባች፡፡
‹‹እንደዛ ከሆነ እኔ ቀድሜሽ ወደቤት ልሂድና ቡናውን እያስፈላው እጠብቅሻለው፡፡››አለቻት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ ቤተሰብ።
👇Sebscribe እያደረጋጁ ቤተሰቦች 500 እንደሰማይ ራቀን ቀረብ አድርጉን😃
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose