ከዛ መዝሙር መዘመር ጀመረ…መዝሙሩ ለእሷ አዲስ ነበር ፣ዜማው ግን ደስ ስለሚል
በተመስጦ ነበር ስታዳምጥ የነበረው…ሁለተኛውን መዝሙር ግን ከልቧ ነበር ስትዘምር የነበር …
ልጅ እያለች ጀምሮ ሁልጊዜም በመዝሙሩ ትደሰት ነበር፣
ሰባኪው ስብከቱን ሲጀምር ሁሉም በፀጥታ ማዳመጥ ጀመሩ
///
…. እግዚአብሔር በህይወታችን ስለሚያደርገው ነገር እንበሳጫለን። እኛን ሊያስተምረን እየሞከረ እንደሆነ አይገባንም። እግዚአብሔርን ችላ ለማለት ልንሞክር እንችላለን፣ነገር ግን ያንን ማድረግ በግድግዳው ላይ‹‹ጨለማ››የሚለውን ቃል በመጻፍ ብርሃንን ለማስወገድ እንደመሞከር ነው። በችግር እና በስቃይ ውስጥ ልንሆን እንችላለን፣ ነገር ግን ‹‹እግዚአብሔር በሹክሹክታ በሕሊናችን ይናገራል .. በሥቃያችን ምክንያት የሚያሰማው ጩኻት መስማት የተሳነውን ዓለም ለመቀስቀስ የሚጠቀምበት የእሱ ሜጋፎን ነው። ህመማችን እና ሀዘናችን የእኛን የፈዘዘ ትኩረት የሚስብበት መንገድ ይሆናል ብዬ አምናለሁ። ራሳችንን የቻልን ፍጥረታት ነን ብለን ስለምናስብ… ሁሉንም ነገር በራሳችን ማድረግ እንደምንችል እናስባለን. ከእግዚአብሔር ተለይተን መኖር የምንችል ይመስለናል ይህም የአበባው ሽታ ከአበባው ለመለየት እንደመሞከር ነው። እግዚአብሔር ሁል ጊዜ አለ እና የህይወታችንን ቁጥጥር ለእርሱ አሳልፈን እንድንሰጥ እየጠበቀን ነው።
ራሄል ስብከቱ ለእሷ ታቅዶ የተዘጋጀ መስሎ ተሰማት…ኪሩቤል ከሞተ በኃላ እግዚአብሔር የሚናገራትን ነገር ሁሉ ላለመስማት ጆሮዋን ዘጋች። የህይወቷ የበላይ ለመሆን እና ለመቆጣጠር ጣረች።ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ፣ በህይወቷ ውስጥ የተከሰቱት ክስተቶች ይህ ምን ያህል ከንቱ እንደሆነ አሳይቷታል።ግን ሌላ ምን ማድረግ ነበረባት? እሷ ፋውንዴሽን ውስጥ መልካም ነገር እየሰራች ነበር. ሰዎችን ከችግራቸው ለማላቀቅ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በስራዋ ላይ ይደገፋሉ.
ሰባኪው ስብከቱን ቀጥሏል ….
..እኛ በሕይወታችን ውስጥ ኃላፊ እንደሆንን በማሰብ፣እንዴት ራሳችንን እንዲህ እናቆስላለን? በእውነቱ እኛ የራሳችን ህይወት ሀለቆች አይደለንም…አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር የራሳችንን መንገድ ለማወቅ እንድንችል በራሳችን መንገድ እንድንሄድ ይፈቅድልናል። ነፍሶች ወደርሱ እስኪጠጉ ድረስ ዕረፍት የላቸውም። ስለዚህ አሁን በመዝሙራዊው ዳዊት መዝሙረ 139፡6 ላይ ባለው የእግዚያብሄር ቃል የእለቱን ትምህርታችንን እንዘጋለን፡፡
‹‹በሰማይእና በምድር በባሕር እና በጥልቆች ሁሉ፣እግዚያብሄር የወደደውን ሁሉ አደረገ ..
….››ቃላቱ በህንፃው ውስጥ ተስተጋብተው በራሔል ልብ ውስጥ አረፉ። ለእግዚአብሔር ጀርባዋን ሰጥታው ነበር። አላመነችበትም ነበር። እና ይህ ሁሉ ቢሆንም ፣ በእሷ ውስጥ ግልፅ የሆነ እረፍት አልነበረም…. ያለ ምንም ጥርጣሬ፣ እግዚአብሔር የለም ማለት አልቻለችም።አዎ ለአመታት በኪሩቤል ሞት አዝናለች… አዎ…እሱን እንዴት እንዳጣችው በማሰብ አሁንም ለብስጭት እና ተስፋ ለመቁረጥ ተጋላጭ እንድትሆን አድርጓታል። አሁንም አምላክ ለምን ጸሎቷን እንዳልመለሰላት ግራ ተጋብታለች። ለዚያ መልሱን አላወቀችም። ነገር ግን በሕይወቷ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት እንዲህ በቀላሉ መካድ እንደማትችል ታውቃለች። ዛሬ የእሱ የተለመደ መነካካት ተሰምቷታል። የመጨረሻው መዝሙር ሲዘመር ፀጋን አቀፈቻትና ከማንም ሰው በመራቅ ከምዕመናኑ መሀከል ሾልካ ወጣች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በተመስጦ ነበር ስታዳምጥ የነበረው…ሁለተኛውን መዝሙር ግን ከልቧ ነበር ስትዘምር የነበር …
ልጅ እያለች ጀምሮ ሁልጊዜም በመዝሙሩ ትደሰት ነበር፣
ሰባኪው ስብከቱን ሲጀምር ሁሉም በፀጥታ ማዳመጥ ጀመሩ
///
…. እግዚአብሔር በህይወታችን ስለሚያደርገው ነገር እንበሳጫለን። እኛን ሊያስተምረን እየሞከረ እንደሆነ አይገባንም። እግዚአብሔርን ችላ ለማለት ልንሞክር እንችላለን፣ነገር ግን ያንን ማድረግ በግድግዳው ላይ‹‹ጨለማ››የሚለውን ቃል በመጻፍ ብርሃንን ለማስወገድ እንደመሞከር ነው። በችግር እና በስቃይ ውስጥ ልንሆን እንችላለን፣ ነገር ግን ‹‹እግዚአብሔር በሹክሹክታ በሕሊናችን ይናገራል .. በሥቃያችን ምክንያት የሚያሰማው ጩኻት መስማት የተሳነውን ዓለም ለመቀስቀስ የሚጠቀምበት የእሱ ሜጋፎን ነው። ህመማችን እና ሀዘናችን የእኛን የፈዘዘ ትኩረት የሚስብበት መንገድ ይሆናል ብዬ አምናለሁ። ራሳችንን የቻልን ፍጥረታት ነን ብለን ስለምናስብ… ሁሉንም ነገር በራሳችን ማድረግ እንደምንችል እናስባለን. ከእግዚአብሔር ተለይተን መኖር የምንችል ይመስለናል ይህም የአበባው ሽታ ከአበባው ለመለየት እንደመሞከር ነው። እግዚአብሔር ሁል ጊዜ አለ እና የህይወታችንን ቁጥጥር ለእርሱ አሳልፈን እንድንሰጥ እየጠበቀን ነው።
ራሄል ስብከቱ ለእሷ ታቅዶ የተዘጋጀ መስሎ ተሰማት…ኪሩቤል ከሞተ በኃላ እግዚአብሔር የሚናገራትን ነገር ሁሉ ላለመስማት ጆሮዋን ዘጋች። የህይወቷ የበላይ ለመሆን እና ለመቆጣጠር ጣረች።ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ፣ በህይወቷ ውስጥ የተከሰቱት ክስተቶች ይህ ምን ያህል ከንቱ እንደሆነ አሳይቷታል።ግን ሌላ ምን ማድረግ ነበረባት? እሷ ፋውንዴሽን ውስጥ መልካም ነገር እየሰራች ነበር. ሰዎችን ከችግራቸው ለማላቀቅ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በስራዋ ላይ ይደገፋሉ.
ሰባኪው ስብከቱን ቀጥሏል ….
..እኛ በሕይወታችን ውስጥ ኃላፊ እንደሆንን በማሰብ፣እንዴት ራሳችንን እንዲህ እናቆስላለን? በእውነቱ እኛ የራሳችን ህይወት ሀለቆች አይደለንም…አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር የራሳችንን መንገድ ለማወቅ እንድንችል በራሳችን መንገድ እንድንሄድ ይፈቅድልናል። ነፍሶች ወደርሱ እስኪጠጉ ድረስ ዕረፍት የላቸውም። ስለዚህ አሁን በመዝሙራዊው ዳዊት መዝሙረ 139፡6 ላይ ባለው የእግዚያብሄር ቃል የእለቱን ትምህርታችንን እንዘጋለን፡፡
‹‹በሰማይእና በምድር በባሕር እና በጥልቆች ሁሉ፣እግዚያብሄር የወደደውን ሁሉ አደረገ ..
….››ቃላቱ በህንፃው ውስጥ ተስተጋብተው በራሔል ልብ ውስጥ አረፉ። ለእግዚአብሔር ጀርባዋን ሰጥታው ነበር። አላመነችበትም ነበር። እና ይህ ሁሉ ቢሆንም ፣ በእሷ ውስጥ ግልፅ የሆነ እረፍት አልነበረም…. ያለ ምንም ጥርጣሬ፣ እግዚአብሔር የለም ማለት አልቻለችም።አዎ ለአመታት በኪሩቤል ሞት አዝናለች… አዎ…እሱን እንዴት እንዳጣችው በማሰብ አሁንም ለብስጭት እና ተስፋ ለመቁረጥ ተጋላጭ እንድትሆን አድርጓታል። አሁንም አምላክ ለምን ጸሎቷን እንዳልመለሰላት ግራ ተጋብታለች። ለዚያ መልሱን አላወቀችም። ነገር ግን በሕይወቷ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት እንዲህ በቀላሉ መካድ እንደማትችል ታውቃለች። ዛሬ የእሱ የተለመደ መነካካት ተሰምቷታል። የመጨረሻው መዝሙር ሲዘመር ፀጋን አቀፈቻትና ከማንም ሰው በመራቅ ከምዕመናኑ መሀከል ሾልካ ወጣች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡
‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች.. ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣ ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።
ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች… ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››
‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››
‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››
ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡
‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡
‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡
‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡
‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ ፈልጌ ነበር.››
‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ ወንበርና ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡
‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡
ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡
በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ, ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።
‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››
‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››
‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።
‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››
‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።
‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።
የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡
‹‹በቂ ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው… ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።
ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ
‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው የፈቀደልኝ የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡
‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች.. ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣ ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።
ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች… ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››
‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››
‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››
ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡
‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡
‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡
‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡
‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ ፈልጌ ነበር.››
‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ ወንበርና ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡
‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡
ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡
በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ, ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።
‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››
‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››
‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።
‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››
‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።
‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።
የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡
‹‹በቂ ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው… ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።
ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ
‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው የፈቀደልኝ የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
እርግጠኛ ያልሆነውን ስሜት ወደ ጎን ገሸሽ አድርጎ በአዘኔታ ስሜት እጇን ያዛት።የሚገርመው ጣቶቿን ዘርግታለት እንደፈለገው እንዲያፍተለትላት ፈቀደችለት… ፣ እና ቀስ በቀስ በልቡ ውስጥ ለእሷ ሚሆን ቦታ ሲከፈት ታወቀው።
ኤልያስ ቀና ብሎ ተመለከታት …አንድ የእንባ ዘለላ በጉንጯ ላይ ሲንሸራተት በማየቱ ተገረመ። ወደራሱ አስጠጋትና ቀስ ብሎ ጠረገላት።
‹‹ይቅርታ››አለች በሹክሹክታ። ወደ ኋላ ዞራ ተመለከተች። እጇን ከእጁ አውጥታ ወደ ፀጋ አመራች።በእነዚህ ጥቂት ጊዜያት ጥቂት ሰዎች እንዳዩ የጠረጠረውን የራሷን ክፍል እንዳሳየችው ተረዳ።
ራሄል ኩኪሶችን በሰሀን አድርጋ ስታቀራርብ ዔሊ ቡናውን ቀዳ ፡፡የተለያዩ ስሜቶች በእሱ ውስጥ እየተሽከረከሩ ነበር። ስለ ኪሩቤል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ስለ ራሄል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ቢሆንም ግን የእርሷን መመሪያ መከተል እንዳለበት ያውቅ ነበር….ለዚህ ነው የበለጠ እንድታወራ ሊጎተጉታት ያልፈቀደው፡፡
‹‹ቡናው ጥሩ መዓዛ አለው››አላት፡፡
‹‹አመሰግናለው››አለችና .. ለፀጋ ኩኪስ ሰጥታ ብርጭቆዋን ወሰደች።በሻይ እየነከረች ታጎርሳት ጀመር፡፡
ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተል ከቆየ በኃላ‹‹ጥሩ እናት ይወጣሻል ››አላት
‹‹..ቢያንስ እየተማርኩ ነው››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹አዎ…የሚገርመው እኮ እናትነት ቀድመሽ ተምረሽ ካወቅሽ በኃላ አይደለም እናት የምትሆኚው….በድንገት እናት ትሆኚያለሽ ከዛ የግድሽን ትማሪያለሽ…ይሄ አንቺን ብቻ ሳይሆን ሁሉም እናቶች የሚያጋጥማቸው ነው፡፡አይደለም ለመጀመሪያ ጊዜ ልጅ ስትወልጂ ይቅርና….የመጀመሪያ ልጅ ከሁለተኛ ልጅ..ሁለተኛው ልጅ ከሶስተኛው ልጅ በፀባይ ..በሚወዳቸውና በሚጠላቸው ነገሮች በብዙ ብዙ ነገር ስለሚለያይ በእያንዳንዱ ልጅ በማሳደግ ሄደት ውስጥ የተለየ አይነት ልምድ ነው የምታገኚው… ››
‹‹አረ ከባድ ነው…..አይደለም ሁለት ሶስት አንዱም ከባድ ነው›››አለችው፡፡
ጥቂት ተጨማሪ ጥያቄዎችን ጠየቃት እና ንግግራቸው በቀላሉ ከስራ ወደ ቤተሰብ ተዛወረ።
እሱም ልክ እንደ እሷ ያደገው በክርስቲያን ቤት ውስጥ እንደሆነ ነገራት። እንደ እሱ፣ እሷም ምንም አይነት የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያዎች አልነበራትም።ስለ ወላጆቹ ጠየቀችው።ስለ አሳዳጊዎቹ ነገራት። እና ስለስጋ ወላጆቹም አወራት፡፡ .
‹‹አሁንም ታስታውሳቸዋለህ?››ራሄል ጠየቀች፣ የፀጋን እጆች እርጥብ በሆነ ፎጣ ለመጥረግ ጎንበስ አለች።
‹‹በመኪና አደጋ ሲሞቱ ስድስት አመቴ ነበር:: ዔሊ በእጁ ጀርባ ላይ የተጋደመውን ጠባሳ ተመለከተ።‹‹እኔ ብቸኛ ልጅ ነበርኩ እና በሕይወት የተረፈኩት እኔ ብቻ ነኝ.››
‹‹ስለዚህ አንተም ሀዘንን ታውቃታለህ ማለትነው.››
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር››
‹‹አዎ። ግን እነሱ የስጋ ወላጆችህ ስለሆኑ ትዝታቸው እና ሀዘኑ ከውስጥህ መቼም አይጠፋም ።››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ››
‹‹እናቴና አባቴ ይህችን ትንሽ ልጅ በጣም እንደሚወዷት አውቃለሁ፣ ነገር ግን እሷ አሁንም አንዳንድ ታሪክ ያላት ሰው ሆና ነው ወደ እነርሱ የመጣቸው…ይታይህ የስድስት አመት ልጅ ሆና ቢሆን ኖሮ በጣም ጠንካራ ትዝታ ይኖራት ነበር ብዬ አስባለሁ። ››
‹‹እኔ ግን ወላጆቼ ሞተዋል. ትዝታዎች ብቻ ናቸው የቀሩኝ…. ለማንኛውም ስለግንኙነት ብዙ ነገር አላውቅም ትያለሽ ግን ሌላ የማስበውን ነገር ሰጥተሺኛል፡፡: ትርጉም ያለው ነገር ነው የተናገርሽው:››
ፈገግ አለችለት…ፈገግታዋ ሳበው። የሆነ ነገር ልትለው አፏን ስትከፍት የእሱ ስልክ ጠራ….
‹‹ይቅርታ ይህ ሆስፒታል ስልክ ነው…ማንሳት አለብኝ። ››
አነሳና አናገረ..ዘጋውና ወደእሷ ዞረ፡፡
‹‹አዝናለው ጥያችሁ ልሄድ ነው…..ችግር አጋጥሞት መግባት ያልቻለ ዶክተር አለ…የእሱን ተራ መሸፈን አለብኝ…እንዲህ ከእናንተ ጋር እደምገናኝ ስላላወቅኩ ቀድሜ ነው ቃል የገባሁለት››
‹‹አረ ችግር የለውም ..እስከአሁን አብረኸን ስለቆየህ በጣም ደስ ብሎናል››አለችው
ሁለቱንም ተሰናበተ እና ሄደ…ራሄል ከእይታዋ እስኪሰወር በትኩረት እያየችው ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ኤልያስ ቀና ብሎ ተመለከታት …አንድ የእንባ ዘለላ በጉንጯ ላይ ሲንሸራተት በማየቱ ተገረመ። ወደራሱ አስጠጋትና ቀስ ብሎ ጠረገላት።
‹‹ይቅርታ››አለች በሹክሹክታ። ወደ ኋላ ዞራ ተመለከተች። እጇን ከእጁ አውጥታ ወደ ፀጋ አመራች።በእነዚህ ጥቂት ጊዜያት ጥቂት ሰዎች እንዳዩ የጠረጠረውን የራሷን ክፍል እንዳሳየችው ተረዳ።
ራሄል ኩኪሶችን በሰሀን አድርጋ ስታቀራርብ ዔሊ ቡናውን ቀዳ ፡፡የተለያዩ ስሜቶች በእሱ ውስጥ እየተሽከረከሩ ነበር። ስለ ኪሩቤል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ስለ ራሄል የበለጠ ለማወቅ ፈልጎ ነበር። ቢሆንም ግን የእርሷን መመሪያ መከተል እንዳለበት ያውቅ ነበር….ለዚህ ነው የበለጠ እንድታወራ ሊጎተጉታት ያልፈቀደው፡፡
‹‹ቡናው ጥሩ መዓዛ አለው››አላት፡፡
‹‹አመሰግናለው››አለችና .. ለፀጋ ኩኪስ ሰጥታ ብርጭቆዋን ወሰደች።በሻይ እየነከረች ታጎርሳት ጀመር፡፡
ሁኔታዋን በትኩረት ሲከታተል ከቆየ በኃላ‹‹ጥሩ እናት ይወጣሻል ››አላት
‹‹..ቢያንስ እየተማርኩ ነው››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹አዎ…የሚገርመው እኮ እናትነት ቀድመሽ ተምረሽ ካወቅሽ በኃላ አይደለም እናት የምትሆኚው….በድንገት እናት ትሆኚያለሽ ከዛ የግድሽን ትማሪያለሽ…ይሄ አንቺን ብቻ ሳይሆን ሁሉም እናቶች የሚያጋጥማቸው ነው፡፡አይደለም ለመጀመሪያ ጊዜ ልጅ ስትወልጂ ይቅርና….የመጀመሪያ ልጅ ከሁለተኛ ልጅ..ሁለተኛው ልጅ ከሶስተኛው ልጅ በፀባይ ..በሚወዳቸውና በሚጠላቸው ነገሮች በብዙ ብዙ ነገር ስለሚለያይ በእያንዳንዱ ልጅ በማሳደግ ሄደት ውስጥ የተለየ አይነት ልምድ ነው የምታገኚው… ››
‹‹አረ ከባድ ነው…..አይደለም ሁለት ሶስት አንዱም ከባድ ነው›››አለችው፡፡
ጥቂት ተጨማሪ ጥያቄዎችን ጠየቃት እና ንግግራቸው በቀላሉ ከስራ ወደ ቤተሰብ ተዛወረ።
እሱም ልክ እንደ እሷ ያደገው በክርስቲያን ቤት ውስጥ እንደሆነ ነገራት። እንደ እሱ፣ እሷም ምንም አይነት የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያዎች አልነበራትም።ስለ ወላጆቹ ጠየቀችው።ስለ አሳዳጊዎቹ ነገራት። እና ስለስጋ ወላጆቹም አወራት፡፡ .
‹‹አሁንም ታስታውሳቸዋለህ?››ራሄል ጠየቀች፣ የፀጋን እጆች እርጥብ በሆነ ፎጣ ለመጥረግ ጎንበስ አለች።
‹‹በመኪና አደጋ ሲሞቱ ስድስት አመቴ ነበር:: ዔሊ በእጁ ጀርባ ላይ የተጋደመውን ጠባሳ ተመለከተ።‹‹እኔ ብቸኛ ልጅ ነበርኩ እና በሕይወት የተረፈኩት እኔ ብቻ ነኝ.››
‹‹ስለዚህ አንተም ሀዘንን ታውቃታለህ ማለትነው.››
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር››
‹‹አዎ። ግን እነሱ የስጋ ወላጆችህ ስለሆኑ ትዝታቸው እና ሀዘኑ ከውስጥህ መቼም አይጠፋም ።››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ››
‹‹እናቴና አባቴ ይህችን ትንሽ ልጅ በጣም እንደሚወዷት አውቃለሁ፣ ነገር ግን እሷ አሁንም አንዳንድ ታሪክ ያላት ሰው ሆና ነው ወደ እነርሱ የመጣቸው…ይታይህ የስድስት አመት ልጅ ሆና ቢሆን ኖሮ በጣም ጠንካራ ትዝታ ይኖራት ነበር ብዬ አስባለሁ። ››
‹‹እኔ ግን ወላጆቼ ሞተዋል. ትዝታዎች ብቻ ናቸው የቀሩኝ…. ለማንኛውም ስለግንኙነት ብዙ ነገር አላውቅም ትያለሽ ግን ሌላ የማስበውን ነገር ሰጥተሺኛል፡፡: ትርጉም ያለው ነገር ነው የተናገርሽው:››
ፈገግ አለችለት…ፈገግታዋ ሳበው። የሆነ ነገር ልትለው አፏን ስትከፍት የእሱ ስልክ ጠራ….
‹‹ይቅርታ ይህ ሆስፒታል ስልክ ነው…ማንሳት አለብኝ። ››
አነሳና አናገረ..ዘጋውና ወደእሷ ዞረ፡፡
‹‹አዝናለው ጥያችሁ ልሄድ ነው…..ችግር አጋጥሞት መግባት ያልቻለ ዶክተር አለ…የእሱን ተራ መሸፈን አለብኝ…እንዲህ ከእናንተ ጋር እደምገናኝ ስላላወቅኩ ቀድሜ ነው ቃል የገባሁለት››
‹‹አረ ችግር የለውም ..እስከአሁን አብረኸን ስለቆየህ በጣም ደስ ብሎናል››አለችው
ሁለቱንም ተሰናበተ እና ሄደ…ራሄል ከእይታዋ እስኪሰወር በትኩረት እያየችው ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
___
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው ጠቀለለቻት።
ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡ ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡
በዛው ቅፅበት የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…
‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር ኤልያስ ነበረ፡፡
ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››
‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት
‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››
‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡
ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››
‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››
‹‹እሺ ይህችን ልጅ ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››
‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡
ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡
የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››
‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››
ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››
‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው። ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።
መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።
‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
___
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው ጠቀለለቻት።
ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡ ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡
በዛው ቅፅበት የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…
‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር ኤልያስ ነበረ፡፡
ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››
‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት
‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››
‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››
‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡
ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››
‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››
‹‹እሺ ይህችን ልጅ ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››
‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡
ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡
የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››
‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››
ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››
‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው። ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።
መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።
‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
ራሄል በትህትና ፈገግ ብላ የዘረጋችውን እጅ ጨበጠችና ወደኃላዋ ዞር ብላ‹‹ ዶ/ር ዔሊያስ ይባላል…እሷ ደግሞ እህቴ ነች››በማለት አስተዋወቀቻቸው፡፡ቀጠለችናም‹‹ከሁለት ሳምንት በፊት እናታችን ወድቃ እግሯን ተሰብሮ ህክምና ላይ ስላለች እህቴን ፀጋን እየተንከባከብኳት ነው…ዶ/ር ደግሞ የእሷ ሀኪም ነው …።››
ፀጋ ለታላቅዋ ሴት ብሩህ ፈገግታ ሰጠቻት ‹‹እንዴት የምታምር ልጅ ነች… ወላጆችሽ ትንሽ ልጅ እያሳደጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ። ሴሬብራል ፓልሲ አለባት አይደል?››
‹‹አዎ ››ስትል መለሰች ራሄል።
‹‹ልዩ ፍላጎት ያለው ህፃን በማደጎ ለመውሰድ መወሰናቸውን ስሰማ አእምሮአቸውን የሳቱ መስሎኝ ነበር፣ነገር ግን አሁን ሳያት ጠንካራ የጤና እክል ቢኖርባትም ለምን እርሷን ለማሳደግ እንደወሰኑ አሁን ገባኝ.. ።ተቀመጡ.. ምን ይምጣ ቡና? ጣፋጭ ሻይ? ለትንሿ ሴት ጭማቂ?››
ሁሉም ወንበር ይዘው እየተቀመጡ‹‹እኔ ሻይ እጠጣለሁ እና ለፀጋ የአፕል ወይም የብርቱካን ጭማቂ ብታገኝ ትደሰታለች››አለች ፡፡ኤሊያስ ሁለቱንም አልተቀበለም።ወይዘሮዋ ትዕዛዙን ለሰራተኞቾ አስተላለፈች፡፡
ያዘዙት መጠጥ መጣላቸው…ኤልያስ ጭማቂውን ወስዶ ፀጋን ያጠጣት ጀመር፡፡
ራሄል ከኤሊያስ ጸጋን ልትቀበለው ስትለ‹‹ችግር የለውም እኔ አጠጣታለው…እንደውም ግቢውን ዞር ዞር እያልን እያየን ጭማቂያችንን ብንጠጣ ጥሩ ይመስለኛል…ችግር የለውም አይደል ወ.ሮ ላምሮት?፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም …እንደፈለጋችሁ ዘና በሉ››
ተነሳና በአንድ እጁ ጭማቂውን በሌላ እጁ ፀጋን ይዞ ከእነሱ እራቅ ብሎ ወደ አትክልት ስፍራው በጥልቀት ገባ…
ወ.ሮ ላምሮት ከፀጋ ጋር አይኗቾ ተንከራተቱ ..ከዛ ድንገት መናገር ጀመረች‹‹እኛ ..ማለቴ እኔና ባሌ ልጆች አልነበረንም። ››በማለት ትካዜ ውስጥ ገባች፡፡
ራሄል እንደመደነጋገር አላትና ‹‹አንድ ጊዜ ልጅ ነበረሽ አይደል?›› ስትል ድንገት ከአፏ አመለጣትና ጠየቀቻት፡፡
‹‹አዎ ነበረኝ…ገና የሶስት አመት ልጅ ነበር። ከዚህች ከአንቺ እህት ትንሽ ይበልጣል››አለች
‹‹ምን ሆነ?›› ራሄል ጠየቀች፣
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር. ረጅም ጊዜ.… ሊገለጽ የማይችል በሽታ ነበረበት..ድንገት ታመመና ሞተብኝ…ምንም ልረዳው አልቻልኩም ››
ራሄልን በሀዘን ፈገግታ ተመለከተቻት።
‹‹ ይገባኛል›› አለች ራሄል ። የራሷን ህመም በወ.ሮዋ አይን ውስጥ ማየት ቻለች። ፡፡
ወ.ሮ ላምሮት በጣቷ ላይ ያለውን ቀለበት ማዞር በመቀጠል. ‹‹እንደገና ሞክረን ነበር… ግን አልተሳካልንም..አንድን ሰው መውደድ ሁልጊዜ እድል ነው. ግን ደግሞ ህመም ሊያመጣ እንደሚችልም ቀድመን አውቀን መዘጋጀት አለብን››
‹‹ለማንኛውም፣ ያ ያለፈው ታሪክ ነው››አለች ወይዘሮዋ፣ እጆቿን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች፣ ቀለበቷ መስታወቱ ላይ አስተጋባ። ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ለመወያየት ወደዚህ እንዳልመጣሽ እርግጠኛ ነኝ። ››ወደ ራሄል መለስ ብላ ተመለከተች፣
ቀጠለች‹‹ፋውንዴሽኑ በዚህ አመት ከእኔ የሚያገኘውን ገንዘብ ምን አይነት ቁምነገር ላይ ለማዋል እንዳሰበ ወይንም ለየትኞቹ የበጓ አድራጎት ድርጅቶች ለማከፋፈል እቅድ እንዳወጣና ….ብሩን ካከፋፈለ ብኃላ አፈፃፀማቸውን እንዴት መከታተል እንዳሰብ እንድታብራሪልኝ ነው የምፈልገው››አለቻት፡፡
ራሄል‹‹ጥሩ›› ብላ የተዘጋጀችበትን ወረቀት አውጥታ አንድ በአንድ እየተነተነች ለ30ደቂቃ ያህል አብራራችላት፡፡
‹‹ጥሩ ነው..ማለቴ ስራችሁ በደንብ የታቀደበት ይመስላል..ግን የበጎ አድራጎት ድርጅቷችን ዝርዝር ስትገልጪልን በቀደም ያንቺ ሰራተኛ እዚህ መታ ካስረዳችኝ ጋር ልዩነት ያለው መሰለን፡፡እሷ በዚህ አመት ስለተመሰረተው ጎህ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት አስረድታኝ ነበር..አብዛኛውን ብር ለዛ ድርጅት ልትሰጡ እንዳሰባችው ነበር የተነገረኝ፡፡››
‹‹ጎህ!!››ራሄል ድንግርግሯ ወጣ…እደዚህ አይነት በጎ አድራጎት ድርጅት መኖሩንም ዛሬ መስማቷ ነው፡፡
‹‹ሮቤል ነው አይደል…ምን ነገረሽ?››ፊቷን አኳሳትራ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ.. ንግግሩን ሁሉ ያደረገችው ወጣቷ ሴት ነበረች። እዚህ በየቦታው የተጣሉ ህጻናትን የሚሰበሰቡ እና እነሱን በእንክብካቤ የሚያሳድጉ ድርጅት በመሆናቸው ሀሳብን ወድጄዋለሁ።››
ራሄል ‹‹ይህ ቡድን በእኔ ተመርምሮ አያውቅም››ንዴቷ እየጨመረ ሄደ።
‹‹ምን ማለትሽ ነው?››ወ.ሮ ላምሮት አሁን ግራ የተጋባች ይመስላል።
‹‹የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ወይም ገንዘባቸውን ለማሰባሰብ የሚያመለክቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በትክክለኛው መንገድ ስራቸውን እንደሚሰሩ እና ከፍተኛ የአስተዳደር ወጪዎችን እንደማይከፍሉ ቀድመን እናረጋግጣለን። አንዳንድ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች አሉ እስከ ሰማንያ በመቶ የአስተዳደር ወጪዎችን የሚከፍሉ በመሆናቸው ለተረጂዎች የሚደርሰው እርዳታ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ፡፡ለማንኛውም ይሁንታ አልሰጧሻትም አይደል?››
‹‹አላደረግኩትም።ከንቺ ጋር ቀድሜ ልነጋገር ብዬ እንጂ ላደርገው ፈልጌ ነበር።››
ራሄል በእፎይታ ተነፈሰች..በገዛ ረዳቷ ተጭበርብራ የአገር መሳቂያ ሆና ነበር፡፡
‹‹ስላላደረግሽው ደስ ብሎኛል፡ እኔ በግሌ ያልመረመርኩትን ማንኛውንም ድርጅት በፍጹም እንደማልመክርሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ። እና ይሄ ትልቅ የገንዘብ ጉድጓድ ነው፤ብሩን ካንቺ ስንረከብ ኃላፊነትን ነው አብረን የምንረከበው..ለእያንዷንዷ ሳንቲም ተጠያቂዋ እኔ ነኝ። ››
‹‹ልጅቷ ለአንቺ ነው የምትሰራው አይደል?››
‹‹አዎ ረዳቴ ነች ወይም ነበርች››ራሄል ረጅም ትንፋሽ ወስዳ የጣቶቿን ጫፍ እርስ በርሳቸው አሻሸች። ከቀናት በፊት አንድ ሰው ኮምፒተሯን ሰብሮ ሊገባ ሲመሞከር እንደነበር አስተውላለች ፡፡ በዛን ቀን በአካባቢው ያለችው ብቸኛዋ ሰው ሎዛ ነበረች።አሁን ነው ያሳታወሰችው፡፡
‹‹ይህን እንዴት ማድረግ ቻለች? ራሔል በሮቤል ተጠራጥራው ነበር..ሎዛን ግን በፍፅም እንዲህ ታደርጋለች ብላ ግምቱ አልነበራትም ። በሎዛ የክህደት ሀሳብ ትንሽ የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰማት… ወንበሯ ተደገፈች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ፀጋ ለታላቅዋ ሴት ብሩህ ፈገግታ ሰጠቻት ‹‹እንዴት የምታምር ልጅ ነች… ወላጆችሽ ትንሽ ልጅ እያሳደጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ። ሴሬብራል ፓልሲ አለባት አይደል?››
‹‹አዎ ››ስትል መለሰች ራሄል።
‹‹ልዩ ፍላጎት ያለው ህፃን በማደጎ ለመውሰድ መወሰናቸውን ስሰማ አእምሮአቸውን የሳቱ መስሎኝ ነበር፣ነገር ግን አሁን ሳያት ጠንካራ የጤና እክል ቢኖርባትም ለምን እርሷን ለማሳደግ እንደወሰኑ አሁን ገባኝ.. ።ተቀመጡ.. ምን ይምጣ ቡና? ጣፋጭ ሻይ? ለትንሿ ሴት ጭማቂ?››
ሁሉም ወንበር ይዘው እየተቀመጡ‹‹እኔ ሻይ እጠጣለሁ እና ለፀጋ የአፕል ወይም የብርቱካን ጭማቂ ብታገኝ ትደሰታለች››አለች ፡፡ኤሊያስ ሁለቱንም አልተቀበለም።ወይዘሮዋ ትዕዛዙን ለሰራተኞቾ አስተላለፈች፡፡
ያዘዙት መጠጥ መጣላቸው…ኤልያስ ጭማቂውን ወስዶ ፀጋን ያጠጣት ጀመር፡፡
ራሄል ከኤሊያስ ጸጋን ልትቀበለው ስትለ‹‹ችግር የለውም እኔ አጠጣታለው…እንደውም ግቢውን ዞር ዞር እያልን እያየን ጭማቂያችንን ብንጠጣ ጥሩ ይመስለኛል…ችግር የለውም አይደል ወ.ሮ ላምሮት?፡፡››
‹‹አረ ችግር የለውም …እንደፈለጋችሁ ዘና በሉ››
ተነሳና በአንድ እጁ ጭማቂውን በሌላ እጁ ፀጋን ይዞ ከእነሱ እራቅ ብሎ ወደ አትክልት ስፍራው በጥልቀት ገባ…
ወ.ሮ ላምሮት ከፀጋ ጋር አይኗቾ ተንከራተቱ ..ከዛ ድንገት መናገር ጀመረች‹‹እኛ ..ማለቴ እኔና ባሌ ልጆች አልነበረንም። ››በማለት ትካዜ ውስጥ ገባች፡፡
ራሄል እንደመደነጋገር አላትና ‹‹አንድ ጊዜ ልጅ ነበረሽ አይደል?›› ስትል ድንገት ከአፏ አመለጣትና ጠየቀቻት፡፡
‹‹አዎ ነበረኝ…ገና የሶስት አመት ልጅ ነበር። ከዚህች ከአንቺ እህት ትንሽ ይበልጣል››አለች
‹‹ምን ሆነ?›› ራሄል ጠየቀች፣
‹‹ከረጅም ጊዜ በፊት ነበር. ረጅም ጊዜ.… ሊገለጽ የማይችል በሽታ ነበረበት..ድንገት ታመመና ሞተብኝ…ምንም ልረዳው አልቻልኩም ››
ራሄልን በሀዘን ፈገግታ ተመለከተቻት።
‹‹ ይገባኛል›› አለች ራሄል ። የራሷን ህመም በወ.ሮዋ አይን ውስጥ ማየት ቻለች። ፡፡
ወ.ሮ ላምሮት በጣቷ ላይ ያለውን ቀለበት ማዞር በመቀጠል. ‹‹እንደገና ሞክረን ነበር… ግን አልተሳካልንም..አንድን ሰው መውደድ ሁልጊዜ እድል ነው. ግን ደግሞ ህመም ሊያመጣ እንደሚችልም ቀድመን አውቀን መዘጋጀት አለብን››
‹‹ለማንኛውም፣ ያ ያለፈው ታሪክ ነው››አለች ወይዘሮዋ፣ እጆቿን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች፣ ቀለበቷ መስታወቱ ላይ አስተጋባ። ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ለመወያየት ወደዚህ እንዳልመጣሽ እርግጠኛ ነኝ። ››ወደ ራሄል መለስ ብላ ተመለከተች፣
ቀጠለች‹‹ፋውንዴሽኑ በዚህ አመት ከእኔ የሚያገኘውን ገንዘብ ምን አይነት ቁምነገር ላይ ለማዋል እንዳሰበ ወይንም ለየትኞቹ የበጓ አድራጎት ድርጅቶች ለማከፋፈል እቅድ እንዳወጣና ….ብሩን ካከፋፈለ ብኃላ አፈፃፀማቸውን እንዴት መከታተል እንዳሰብ እንድታብራሪልኝ ነው የምፈልገው››አለቻት፡፡
ራሄል‹‹ጥሩ›› ብላ የተዘጋጀችበትን ወረቀት አውጥታ አንድ በአንድ እየተነተነች ለ30ደቂቃ ያህል አብራራችላት፡፡
‹‹ጥሩ ነው..ማለቴ ስራችሁ በደንብ የታቀደበት ይመስላል..ግን የበጎ አድራጎት ድርጅቷችን ዝርዝር ስትገልጪልን በቀደም ያንቺ ሰራተኛ እዚህ መታ ካስረዳችኝ ጋር ልዩነት ያለው መሰለን፡፡እሷ በዚህ አመት ስለተመሰረተው ጎህ የህፃናት ማሳደጊያ ድርጅት አስረድታኝ ነበር..አብዛኛውን ብር ለዛ ድርጅት ልትሰጡ እንዳሰባችው ነበር የተነገረኝ፡፡››
‹‹ጎህ!!››ራሄል ድንግርግሯ ወጣ…እደዚህ አይነት በጎ አድራጎት ድርጅት መኖሩንም ዛሬ መስማቷ ነው፡፡
‹‹ሮቤል ነው አይደል…ምን ነገረሽ?››ፊቷን አኳሳትራ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ.. ንግግሩን ሁሉ ያደረገችው ወጣቷ ሴት ነበረች። እዚህ በየቦታው የተጣሉ ህጻናትን የሚሰበሰቡ እና እነሱን በእንክብካቤ የሚያሳድጉ ድርጅት በመሆናቸው ሀሳብን ወድጄዋለሁ።››
ራሄል ‹‹ይህ ቡድን በእኔ ተመርምሮ አያውቅም››ንዴቷ እየጨመረ ሄደ።
‹‹ምን ማለትሽ ነው?››ወ.ሮ ላምሮት አሁን ግራ የተጋባች ይመስላል።
‹‹የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ወይም ገንዘባቸውን ለማሰባሰብ የሚያመለክቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በትክክለኛው መንገድ ስራቸውን እንደሚሰሩ እና ከፍተኛ የአስተዳደር ወጪዎችን እንደማይከፍሉ ቀድመን እናረጋግጣለን። አንዳንድ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች አሉ እስከ ሰማንያ በመቶ የአስተዳደር ወጪዎችን የሚከፍሉ በመሆናቸው ለተረጂዎች የሚደርሰው እርዳታ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ፡፡ለማንኛውም ይሁንታ አልሰጧሻትም አይደል?››
‹‹አላደረግኩትም።ከንቺ ጋር ቀድሜ ልነጋገር ብዬ እንጂ ላደርገው ፈልጌ ነበር።››
ራሄል በእፎይታ ተነፈሰች..በገዛ ረዳቷ ተጭበርብራ የአገር መሳቂያ ሆና ነበር፡፡
‹‹ስላላደረግሽው ደስ ብሎኛል፡ እኔ በግሌ ያልመረመርኩትን ማንኛውንም ድርጅት በፍጹም እንደማልመክርሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ። እና ይሄ ትልቅ የገንዘብ ጉድጓድ ነው፤ብሩን ካንቺ ስንረከብ ኃላፊነትን ነው አብረን የምንረከበው..ለእያንዷንዷ ሳንቲም ተጠያቂዋ እኔ ነኝ። ››
‹‹ልጅቷ ለአንቺ ነው የምትሰራው አይደል?››
‹‹አዎ ረዳቴ ነች ወይም ነበርች››ራሄል ረጅም ትንፋሽ ወስዳ የጣቶቿን ጫፍ እርስ በርሳቸው አሻሸች። ከቀናት በፊት አንድ ሰው ኮምፒተሯን ሰብሮ ሊገባ ሲመሞከር እንደነበር አስተውላለች ፡፡ በዛን ቀን በአካባቢው ያለችው ብቸኛዋ ሰው ሎዛ ነበረች።አሁን ነው ያሳታወሰችው፡፡
‹‹ይህን እንዴት ማድረግ ቻለች? ራሔል በሮቤል ተጠራጥራው ነበር..ሎዛን ግን በፍፅም እንዲህ ታደርጋለች ብላ ግምቱ አልነበራትም ። በሎዛ የክህደት ሀሳብ ትንሽ የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰማት… ወንበሯ ተደገፈች።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ቤት እንደተመለሱ ቀጥታ ወደራሄል ወላጇቾ ቤት ነው የሄዱት፡፡ኤልያስ ቤት ድረስ አብሯቸው የመጣው በሁለት ምክንያት ነው…አንድም ሊሸኛቸው ሲሆን ሌላው ግን ጥዋት ከቤት ወጥቶ አብሯቸው ሲሄድ ሞተር ሳይክሉን እዛው ጥሎ ስለነበረው የሄደው እሱን ለመውሰድ ነው…"ካለበለዚይ ጥዋት ወደስራ ለመግባት ታኪሲ ፍለጋ መጋፋት ሊጠበቅበት ነው…ያ ደግሞ በጣም የሚጠላው ነገር ነው፡፡
ደርሰው ራሄል መኪናውን ፓርክ አድርጋ እንዳቆመች እሱ ፈጠን ብሎ ወረደና ፀጋን አንስቶ አቀፋት..ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዷት ስለነበረ ሲያቅፍት ልጥፍ አለችበት፡፡ራሄል ቦርሳውን አንስታ አንጠለጠለችና ተከተለቻቸው እና ወደ ግዙፍ ቤት ተከታለው ሲገቡ ጥዋት ተሰምቷት የነበረ ስሜት ተመልሷ ተሰማት…ባሏ… ተወዳጅ ልጇን አቅፎ ወደቤት ሲገቡ….ሀሳቡ የደስታ ውስጧ በደስታ ስሜት እንዲጥለቀለቅ ስላደረጋት ‹‹እንዴት ደስ ይላል››ስትል በለሆሳሳ አንሾካሾከች፡፡ከፊት ቀደመችና ሳሎኑን ሰንጥቃ እየመራች ወደፀጋ ክፍል ይዛው ሄደች… ቶሎ ብላ ብርድ ልብሱን ገለጠችለት…ቀስ ብሎ አስተኛትና ተጋግዘው አለባበሳትና ቆመ…ተከትላው ቆመች…በመሀከላቸው ያለው ርቀት ከአንድሜትር አይበልጥም…አንደኛው ሌለኛው ላይ አፍጥጧል….በሚገርም ሁኔታ የትንፋሽ ማጠር አጋጠማት. …ቀስ እያለ ተጠጋትና እጇቹን በወገቧ ላይ አሳረፈ፡፡
ውርር የሚያደርግ ጥሩ ስሜት ተሰማት…ከዛ በምን ፍጥነት እንደሆነ ሳታውቅ ከንፈሮቹ በእሷ ከንፈር ላይ አረፉ …የራሄል አይኖች ተዘጉ፤ እና ለአፍታ ድንጋጤ ተሰማት ፣ እጆቹ በወገቧ ዙሪያ ተጠመጠሙባት እና ወደራሱ ጎትቶ አስጠጋት። ራሄል ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ በቀጣይ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር የማወቅ ጉጉት ተሰማት። የበለጠ ልትለጠፍበትና ልትደገፍበት ፈቀደች፡፡ ‹‹ይህ ጥሩ ሥነ ምግባር አይደለም?››በውስጧ ነበር ያሰበችው… በድንገት የከበደውን ከባቢ አየር ማቅለል ፈለገች። ለብዙ ዓመታት ሳትወድቅ ከቆየችበት ቦታ ለመመለስ ተፍጨረጨረች።
‹‹የእህቴን ሐኪም መሳም ?››ከእቅፉ ሳትወጣ የሹክሹክታ ድምፅ አሰማች።ወደፊቷ የተደፋውን ፀጉሯን ወደኃላ በመመለስ አስተካከለላት፡፡ከዚያም , ቀስ ብሎ ከከንፈሯም ከአካሏ ተላቀቀ እና እራቅ አለ።
‹‹ ፀጋ ቅሬታ እንደማታቀርብ አምናለው››አለችና ዓይኗን በእፍረት ደፍች፡፡ ለእሱ ያላትን መስህብ በውስጧ መቅበር እስከቻለች ድረስ፣ እራሷን ከእሱ ለይታ ማቆየት እስከቻለች ድረስ፣ እነዚህን አዳዲስ እና አደገኛ ስሜቶች መቋቋም እንደምትችል ታስብ ነበር።አሁን ግን?በጣም ለረጅም ጊዜ የናፈቀችውን ነገር ቀምሳለች። ከንፈሯ ላይ መች ተጠግቶ እንደተጣበቀባት እንኳን አላወቀችውም። ፍቃዷን እና ሙሉ ስሜቷን ለዚህ ሰው እስክትሰጥ ቅፅበት ድረስ ልቧን በኪሩቤል የመቃብር ቦታ ለዘመናት ቀብራው ነበር፡፡ በደረሰባት ኪሳራ ተበሳጭታ ስለነበረ ራሷን ዳግመኛ እንደዚህ ላለ ሁኔታ ለማጋለጠ ፈፅሞ እንደማትፈቅድ ቃል ገብታ ነበር። አንድን ሰው በጥልቀት ለመንከባከብ መፍቀድ ራስን ነገ በድንገት ለሚመጣ ህመም ማመቻቸት እንደሆነ ህይወት አስተምራታለች።ከዛ ስቃይ ለማገገም እና እንደገና ወደህይወት ለመመለስ ዓመታት ፈጅቶባታል።
‹‹ይሄ ጉዳይ በጣም ያስፈራኛል።››አለችው፡፡
አገጯን በአውራ ጣት ዳባበሳት እና ‹‹ምንም አይደለም እኔም እፈራለሁ:: ግን ፍርሀታችንን ለማለስለስ ብዙ ጊዜ አለን››አለና ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
በረጅሙ ተነፈሰች፣ ከዚያም ፈገግ አለች።
ጭንቅላቷ ላይ ሳማትና ከዚያም በሹክሹክታ ‹‹ባዬ ራሄል››በማለት ክፍሉንም ቤቱንም ለቆ ወጣ ።ራሄል እስከሳሎን ተከተለችውና ከኋላው በሩን ዘጋች፡፡ የሞተር ሳይክሉን ድምፅ በመኪና መንገዱ ላይ ሲንደቀደቅ ሰማች። ጭንቅላቷን ቀዝቃዛው መስታወት ላይ አስደገፈች፡፡ …በድንገት መጸለይ እንዳለባት ተሰማት።‹‹ጌታ ሆይ እሱን ጠብቀው›› አለች ‹‹ራሷን ለሌላ ሰው በዚህ መንገድ እከፍታለው ብላ ፈፅሞ አስባ አታውቅም ነበር? የፀጋ የታፈነ ጩኸት ተሰማት…ራሷን ከተደገፈችበት መስታወት ቀና አደረገች እና ተንቀሳቀሰች…ከዛ ወደ ፀጋ ሄደች። እህቷን ለመከታተል ወደ ደረጃው እየሮጠች ስትሄድ፣ ቀድሞ የነበረባትን ስሜት እየሰመጠ እንደሆነ ተረዳች።
///
ዔሊያስ የቤቱን ዙሪያ ገባ ተመለከተ። ምንም ያማረ ነገር የለም። በራሱ ቤት ውስጥ በራሱ ሶፋ ላይ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም፣ አእምሮው ከአንድ በሰአት በፊትና በተለያት ሴት ላይ ተጣብቆ ነበር።ከአንድ ሰአት በፊት የሳማት ሴት አሁንም ልቡ ውስጥ እየተገላበጠች ነው።እንደዛ ያለ ድንገተኛ እርምጃ እንዲወስድ ያነሳሳው ምንድን ነበር?ቢያስብ ቢያስብ ሊገለፅለት አልቻለም፡፡
እረፍት አጥቶ ከሶፋው በመነሳት ቢንያም ወደተኛበት ክፍል ተራመደ… ሀሳቡ ዋና መኝታ ቤቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ማለቅ እንዳለበት ሊነግረው ነበር ። ነገሮች እንዳሰበው ሚሄዱ ከሆነ እና የገንዘብ እጥረት ካላጋጠመው ቤቱ በስድስት ወር ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይፈልጋል። በእቅዱ መሰረት ቤቱን ካጠናቀቀ በኃላ ቀጣዩ እቅዱ አዲስ መኪና መግዛት ነው። እና ከዚያ ምናልባት ይህንን ንፁህ እና በስርዓት የተቀነበበ ህይወቱን የምትካፍለው ሴት መፈለግ ይኖርበት ይሆናል። ከአመታ በፊት እቅዱን በዚህ መንገድ በቅደም ተከተል ሲያስቀምጥ ሁሉም ነገር እንከን የለሽ እንደሆነ እርግጠኛ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ ራሔል ከፊቱ ከመጋረጧ በፊት ነበር ።
የወንዱሙን ክፍል ለመክፈት እጄታውን ከያዘ በኃላ ሀሰቡን ቀየረ…ራሴ ተረብሼ ለምን እሱን እረብሸዋለው..በማለት ወደኃላ ተመለሰና ወደራሱ መኝታክፍል ገባ፡፡የልብሱን መሳቢያ ከፍቶ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ቤት ያመጣውን የስጋ ወላጇቹን የፎቶ ሳጥን አወጣ ፡፡ራሄል ያቀረበችለትን ሀሳብ በድጋሚ አሰበበት። ምናልባት አሳዳጊዎቹ ይሄንን የወላጆቹን ፎቶ ከእሱ ለማራቅ ጥሩ ምክንያቶች ነበሯቸው።በወላጆቹ ፊት ላይ የራሱን አሻራ ለማግኘት እየሞከረ ፎቶውን አገላብጧ ተመለከተ። አገጩን በእናቱ፣ ዓይኖቹ በአባቱ መልክ ላይ በጨረፍታ የተመለከተ መስሎት ነበር። ወይም ምናልባት ምኞት እንደዛ ስለሆነ ይሆናል፡፡ ፡፡እሱ እንደ አብዛኛው የማደጎ ልጆች ፣ስለ ወላጆቹ ይበልጥ ለመማር እና ለማወቅ ፍላጎት ነበረው ።እሱን በተመለከተ በህፃናት ማሳደጊያ ተቋሙ ውስጥ ያለው ፋይል ውድ የሆኑ ጥቂት መረጃዎችን የያዘ ሲሆን አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውቅ አድርገውታል፡፡ታዲያ ለምን መርካት አልቻለም?
ራሄል የማንቂያ ሰዓቱን ላይ ባለማመን አፈጠጠች።እንቅልፍ አልወስዳት ብሎ ከግራ ወደቀኝ እየተገላበጠች ለአንድ ሰአት ተሰቃየች… የሰዓቱ መንቀርፈፍ የዘለአለም መሰላት። ደጋግማ ከኤሊ ጋር ስታጫውተው የነበረውን ትዕይንት አዲስ እንደወጣ ተወዳጅ ፊልም ደጋግማ በምልሰት በማሰብ አጣጣመችው፣ የከንፈሮቹን ንክኪ እንደገና ተሰማት።መላልሳ ባሰበችው ቁጥር በእያንዳንዱ ትውስታ አዲስ ስሜት ይሰማት ነበር። በቀጣይ ምንድነው የሚሆነው….?እራሷን ትጠይቃለች….አእምሯዋ ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግራ መጋባት ውስጥ አሽቀንጥሮ ይጥላታል፡፡
ያለፈውን የልቧን ጭለማ ጓዝ እንዴት መልቀቅ እንዳለባት እስከአሁን አላወቀችም፣ አልደፈረችም።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
ከወ.ሮ ላምሮት ቤት እንደተመለሱ ቀጥታ ወደራሄል ወላጇቾ ቤት ነው የሄዱት፡፡ኤልያስ ቤት ድረስ አብሯቸው የመጣው በሁለት ምክንያት ነው…አንድም ሊሸኛቸው ሲሆን ሌላው ግን ጥዋት ከቤት ወጥቶ አብሯቸው ሲሄድ ሞተር ሳይክሉን እዛው ጥሎ ስለነበረው የሄደው እሱን ለመውሰድ ነው…"ካለበለዚይ ጥዋት ወደስራ ለመግባት ታኪሲ ፍለጋ መጋፋት ሊጠበቅበት ነው…ያ ደግሞ በጣም የሚጠላው ነገር ነው፡፡
ደርሰው ራሄል መኪናውን ፓርክ አድርጋ እንዳቆመች እሱ ፈጠን ብሎ ወረደና ፀጋን አንስቶ አቀፋት..ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዷት ስለነበረ ሲያቅፍት ልጥፍ አለችበት፡፡ራሄል ቦርሳውን አንስታ አንጠለጠለችና ተከተለቻቸው እና ወደ ግዙፍ ቤት ተከታለው ሲገቡ ጥዋት ተሰምቷት የነበረ ስሜት ተመልሷ ተሰማት…ባሏ… ተወዳጅ ልጇን አቅፎ ወደቤት ሲገቡ….ሀሳቡ የደስታ ውስጧ በደስታ ስሜት እንዲጥለቀለቅ ስላደረጋት ‹‹እንዴት ደስ ይላል››ስትል በለሆሳሳ አንሾካሾከች፡፡ከፊት ቀደመችና ሳሎኑን ሰንጥቃ እየመራች ወደፀጋ ክፍል ይዛው ሄደች… ቶሎ ብላ ብርድ ልብሱን ገለጠችለት…ቀስ ብሎ አስተኛትና ተጋግዘው አለባበሳትና ቆመ…ተከትላው ቆመች…በመሀከላቸው ያለው ርቀት ከአንድሜትር አይበልጥም…አንደኛው ሌለኛው ላይ አፍጥጧል….በሚገርም ሁኔታ የትንፋሽ ማጠር አጋጠማት. …ቀስ እያለ ተጠጋትና እጇቹን በወገቧ ላይ አሳረፈ፡፡
ውርር የሚያደርግ ጥሩ ስሜት ተሰማት…ከዛ በምን ፍጥነት እንደሆነ ሳታውቅ ከንፈሮቹ በእሷ ከንፈር ላይ አረፉ …የራሄል አይኖች ተዘጉ፤ እና ለአፍታ ድንጋጤ ተሰማት ፣ እጆቹ በወገቧ ዙሪያ ተጠመጠሙባት እና ወደራሱ ጎትቶ አስጠጋት። ራሄል ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ በሙሉ በቀጣይ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር የማወቅ ጉጉት ተሰማት። የበለጠ ልትለጠፍበትና ልትደገፍበት ፈቀደች፡፡ ‹‹ይህ ጥሩ ሥነ ምግባር አይደለም?››በውስጧ ነበር ያሰበችው… በድንገት የከበደውን ከባቢ አየር ማቅለል ፈለገች። ለብዙ ዓመታት ሳትወድቅ ከቆየችበት ቦታ ለመመለስ ተፍጨረጨረች።
‹‹የእህቴን ሐኪም መሳም ?››ከእቅፉ ሳትወጣ የሹክሹክታ ድምፅ አሰማች።ወደፊቷ የተደፋውን ፀጉሯን ወደኃላ በመመለስ አስተካከለላት፡፡ከዚያም , ቀስ ብሎ ከከንፈሯም ከአካሏ ተላቀቀ እና እራቅ አለ።
‹‹ ፀጋ ቅሬታ እንደማታቀርብ አምናለው››አለችና ዓይኗን በእፍረት ደፍች፡፡ ለእሱ ያላትን መስህብ በውስጧ መቅበር እስከቻለች ድረስ፣ እራሷን ከእሱ ለይታ ማቆየት እስከቻለች ድረስ፣ እነዚህን አዳዲስ እና አደገኛ ስሜቶች መቋቋም እንደምትችል ታስብ ነበር።አሁን ግን?በጣም ለረጅም ጊዜ የናፈቀችውን ነገር ቀምሳለች። ከንፈሯ ላይ መች ተጠግቶ እንደተጣበቀባት እንኳን አላወቀችውም። ፍቃዷን እና ሙሉ ስሜቷን ለዚህ ሰው እስክትሰጥ ቅፅበት ድረስ ልቧን በኪሩቤል የመቃብር ቦታ ለዘመናት ቀብራው ነበር፡፡ በደረሰባት ኪሳራ ተበሳጭታ ስለነበረ ራሷን ዳግመኛ እንደዚህ ላለ ሁኔታ ለማጋለጠ ፈፅሞ እንደማትፈቅድ ቃል ገብታ ነበር። አንድን ሰው በጥልቀት ለመንከባከብ መፍቀድ ራስን ነገ በድንገት ለሚመጣ ህመም ማመቻቸት እንደሆነ ህይወት አስተምራታለች።ከዛ ስቃይ ለማገገም እና እንደገና ወደህይወት ለመመለስ ዓመታት ፈጅቶባታል።
‹‹ይሄ ጉዳይ በጣም ያስፈራኛል።››አለችው፡፡
አገጯን በአውራ ጣት ዳባበሳት እና ‹‹ምንም አይደለም እኔም እፈራለሁ:: ግን ፍርሀታችንን ለማለስለስ ብዙ ጊዜ አለን››አለና ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
በረጅሙ ተነፈሰች፣ ከዚያም ፈገግ አለች።
ጭንቅላቷ ላይ ሳማትና ከዚያም በሹክሹክታ ‹‹ባዬ ራሄል››በማለት ክፍሉንም ቤቱንም ለቆ ወጣ ።ራሄል እስከሳሎን ተከተለችውና ከኋላው በሩን ዘጋች፡፡ የሞተር ሳይክሉን ድምፅ በመኪና መንገዱ ላይ ሲንደቀደቅ ሰማች። ጭንቅላቷን ቀዝቃዛው መስታወት ላይ አስደገፈች፡፡ …በድንገት መጸለይ እንዳለባት ተሰማት።‹‹ጌታ ሆይ እሱን ጠብቀው›› አለች ‹‹ራሷን ለሌላ ሰው በዚህ መንገድ እከፍታለው ብላ ፈፅሞ አስባ አታውቅም ነበር? የፀጋ የታፈነ ጩኸት ተሰማት…ራሷን ከተደገፈችበት መስታወት ቀና አደረገች እና ተንቀሳቀሰች…ከዛ ወደ ፀጋ ሄደች። እህቷን ለመከታተል ወደ ደረጃው እየሮጠች ስትሄድ፣ ቀድሞ የነበረባትን ስሜት እየሰመጠ እንደሆነ ተረዳች።
///
ዔሊያስ የቤቱን ዙሪያ ገባ ተመለከተ። ምንም ያማረ ነገር የለም። በራሱ ቤት ውስጥ በራሱ ሶፋ ላይ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም፣ አእምሮው ከአንድ በሰአት በፊትና በተለያት ሴት ላይ ተጣብቆ ነበር።ከአንድ ሰአት በፊት የሳማት ሴት አሁንም ልቡ ውስጥ እየተገላበጠች ነው።እንደዛ ያለ ድንገተኛ እርምጃ እንዲወስድ ያነሳሳው ምንድን ነበር?ቢያስብ ቢያስብ ሊገለፅለት አልቻለም፡፡
እረፍት አጥቶ ከሶፋው በመነሳት ቢንያም ወደተኛበት ክፍል ተራመደ… ሀሳቡ ዋና መኝታ ቤቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ማለቅ እንዳለበት ሊነግረው ነበር ። ነገሮች እንዳሰበው ሚሄዱ ከሆነ እና የገንዘብ እጥረት ካላጋጠመው ቤቱ በስድስት ወር ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይፈልጋል። በእቅዱ መሰረት ቤቱን ካጠናቀቀ በኃላ ቀጣዩ እቅዱ አዲስ መኪና መግዛት ነው። እና ከዚያ ምናልባት ይህንን ንፁህ እና በስርዓት የተቀነበበ ህይወቱን የምትካፍለው ሴት መፈለግ ይኖርበት ይሆናል። ከአመታ በፊት እቅዱን በዚህ መንገድ በቅደም ተከተል ሲያስቀምጥ ሁሉም ነገር እንከን የለሽ እንደሆነ እርግጠኛ ነበር፡፡ ነገር ግን ያ ራሔል ከፊቱ ከመጋረጧ በፊት ነበር ።
የወንዱሙን ክፍል ለመክፈት እጄታውን ከያዘ በኃላ ሀሰቡን ቀየረ…ራሴ ተረብሼ ለምን እሱን እረብሸዋለው..በማለት ወደኃላ ተመለሰና ወደራሱ መኝታክፍል ገባ፡፡የልብሱን መሳቢያ ከፍቶ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ቤት ያመጣውን የስጋ ወላጇቹን የፎቶ ሳጥን አወጣ ፡፡ራሄል ያቀረበችለትን ሀሳብ በድጋሚ አሰበበት። ምናልባት አሳዳጊዎቹ ይሄንን የወላጆቹን ፎቶ ከእሱ ለማራቅ ጥሩ ምክንያቶች ነበሯቸው።በወላጆቹ ፊት ላይ የራሱን አሻራ ለማግኘት እየሞከረ ፎቶውን አገላብጧ ተመለከተ። አገጩን በእናቱ፣ ዓይኖቹ በአባቱ መልክ ላይ በጨረፍታ የተመለከተ መስሎት ነበር። ወይም ምናልባት ምኞት እንደዛ ስለሆነ ይሆናል፡፡ ፡፡እሱ እንደ አብዛኛው የማደጎ ልጆች ፣ስለ ወላጆቹ ይበልጥ ለመማር እና ለማወቅ ፍላጎት ነበረው ።እሱን በተመለከተ በህፃናት ማሳደጊያ ተቋሙ ውስጥ ያለው ፋይል ውድ የሆኑ ጥቂት መረጃዎችን የያዘ ሲሆን አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውቅ አድርገውታል፡፡ታዲያ ለምን መርካት አልቻለም?
ራሄል የማንቂያ ሰዓቱን ላይ ባለማመን አፈጠጠች።እንቅልፍ አልወስዳት ብሎ ከግራ ወደቀኝ እየተገላበጠች ለአንድ ሰአት ተሰቃየች… የሰዓቱ መንቀርፈፍ የዘለአለም መሰላት። ደጋግማ ከኤሊ ጋር ስታጫውተው የነበረውን ትዕይንት አዲስ እንደወጣ ተወዳጅ ፊልም ደጋግማ በምልሰት በማሰብ አጣጣመችው፣ የከንፈሮቹን ንክኪ እንደገና ተሰማት።መላልሳ ባሰበችው ቁጥር በእያንዳንዱ ትውስታ አዲስ ስሜት ይሰማት ነበር። በቀጣይ ምንድነው የሚሆነው….?እራሷን ትጠይቃለች….አእምሯዋ ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግራ መጋባት ውስጥ አሽቀንጥሮ ይጥላታል፡፡
ያለፈውን የልቧን ጭለማ ጓዝ እንዴት መልቀቅ እንዳለባት እስከአሁን አላወቀችም፣ አልደፈረችም።
አእምሮዋ እንደምንም ከኤልያስ ትዝታ ተላቀቀና ወደ እሁድ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ተመለሰ። ሰባኪው እግዚአብሔር ሕይወታቸሁን እንዲቆጣጠር እንዲፈቅዱ እንዴት እንዳበረታታቸው ትዝ አላት።ከተኛችበት ተስፈንጥራ ተነሳች ፤አልጋዋ አጠገብ ያለውን የራስጌ መብራቷን አበራች ፣ ጋወኗን አንስታ ደረበችና ወደ አባቷ ቢሮ ወረደች። ጠረጴዛው በሙሉ በወረቀቶች ተሞልቶ ነበር ፡፡ችላ ብላ አባቷ የሃይማኖት መጽሃፎቹን እንደያዘ ወደምታውቀው መደርደሪያ ሄደች እና መጽሐፍ ቅዱስ አገኘች፡፡ ከመፅሀፍቶቹ መሀከል መዝዛ አወጣች። ወላጆቿ በአልጋቸው አጠገብ የራሳቸው መጽሐፍ ቅዱስ ነበራቸው። ይህ አሁን በእጇ የያዘችው በሠርጋቸው ቀን የተሰጣቸው ጠንካራና በልዩ ቆዳ የተለበጠ ልዩ አይነት ሽፋን ያለው መፅሀፍ ቅዱስ ነው ፡፡ወደ አልጋዋ ተመልሳ ብርድብሱን ገልጣ ገብታ ትራሱን ደገፍ አለችና በግምት ከፈተችና ማንባብ ጀመረች…ማኃልዬ..ማኃልዬ ዘሰለሞን ምዕራፍ-ዠ 2/10
ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ
ወዳጄ ሆይ ተነሺ
ውበቴ ሆይ ነይ
እንሆ ክረምቱ አለፈ
ዝናቡም አልፎ ሄደ
አበቦችም በምድር ላይ ተገለጡ
የዜማም ጊዜ ደረሰ
የቁርዬውም ቃል በምድራችን ተሰማ
በለሱ ጎመራ ወይኖቹም አበቡ
መዓዛቸውንም ሰጡ
ወዳጄ ሆይ ተነሺ
ውበቴ ሆይ ነይ
ደስ የሚል ስሜት ተሰማት…..መፃፍ ቅዱስን ከድና አስቀመጠችና ተከናንባ ተኛች…ጭልጥ ያለ ሰላማዊ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ
ወዳጄ ሆይ ተነሺ
ውበቴ ሆይ ነይ
እንሆ ክረምቱ አለፈ
ዝናቡም አልፎ ሄደ
አበቦችም በምድር ላይ ተገለጡ
የዜማም ጊዜ ደረሰ
የቁርዬውም ቃል በምድራችን ተሰማ
በለሱ ጎመራ ወይኖቹም አበቡ
መዓዛቸውንም ሰጡ
ወዳጄ ሆይ ተነሺ
ውበቴ ሆይ ነይ
ደስ የሚል ስሜት ተሰማት…..መፃፍ ቅዱስን ከድና አስቀመጠችና ተከናንባ ተኛች…ጭልጥ ያለ ሰላማዊ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰተ_በዘሪሁን_ገመቹ
___
//
ዛሬ ጠዋት ሎዛን ከስራ መባረሯን ለመናገር ፀጋን ይዛ ወደ ፋውንዴሽን ቢሮ ሄዳ ነበር፡፡
የሎዛ ክህደት አሁንም እያመማት ነው፣እሷን በመገላገሏ ደስ ብትሰኝም ከእስከአሁኑ በባሰ ሁኔታ፣ የስራ ጫናው ሊጠነክርባት እንደሚችል ተሰምቷታል።እሷ የምትፈልገውን ስራ በእቅዳቸው መሰረት እንዲከወንላት ከፈለገች ሁለት ተጨማሪ ጥንድ እጆች፣ አይኖች እና ጆሮዎች ያስፈልጋታል።
ራሄል በቁጭት እና በንዴት ቢሮ ቁጭ ብላ ከሮቤል ጋር እያወራች ነው፡፡
‹‹ ሮቤል በሆነው ነገር በጣም አዝኛለው…የማፍያ ፀባይ ካላቸው የበጎ አድራጎት ድርጅተች ጋር ተመሳጥራ በእኔ ድርጅት ስም ልትዘረፍ ስትል ነው የያዝኳት››
‹‹አዎ..ከዚህ በፊት የምታደርጋቸው አንዳንድ ሁኔተዎች ሳላላማሩኝ ጥንቀቄ እንድታደርጊ ጠቆም አድርጌሽ ነበረ….ይመስለኛል እንደቁምነገር ወስደሸሽ አላዳመጥሽኝም››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…በጣም እኮ ነበር የማምናት››
‹‹ለማንኛውም ከፍተኛ ኪሳራ ሳታስከትል በጊዜ ስለደረሽባት ጥሩ ነገር ነው….ለወደፊቱ ትምህርት ይሆንሻል››አላት፡፡
‹‹ አዎ ትክክል ነህ…ለማንኛውም አሁን ሌላ ጎበዝ እና ታማኝ ረዳት ማግኘት አለብኝ ፡፡››
‹‹ያንን ስራ በንዑስ ኮንትራት ማሰራት የሚሻል ይመስለኛል››የሚል ምክር ሰጣት፡፡
‹‹አይ ይህ በራሴ ማድረግ አለብኝ።ብቻ በፋውንዴሽኑ ላይ ሌላ ጉዳት እንዳላደረሰች ተስፋ አደርጋለሁ።››
የቢሮውን ስራ ለሮቤል በአደራ ሰጥታ ፀጋን ይዛ ከቢሮ ወጣችና ወደሆስፒታል ነው የሄደችው፡፡ፀጋ ታማ ሳይሆን መደበኛ ክትትል የምታደርግባትን ቀን ስለሆነ ነበር ወደ ሆስፒታል የወሰደቻት..ከዛ በኋላ ነው ወደቤታቸው የተመለሱት፡፡
ራሄል በምትወደው ሶፋ ላይ ተቀምጣ ትራስ በመደግፋ ወረቀቶች እያገላበጠች ሳለ ስልኳ ጠራ..አነሳችና አየችው፡፡አባቷ ናቸው፡፡በጭኗ ላይ ያሉትን ወረቀቶች ማገለባበጧን ሳታቆም አባቷን ማውራት ጀመረች፡፡
‹‹አባዬ እንዴት ነህ..እማዬስ?››
‹‹እናትሽ በጣም ቆራጥ ነች እና ዶክተሮቹ በጤናዋ መሻሻል በጣም ተደስተዋል.››አላት አባቷ፡፡
‹‹ደስ ብሎኛል አባዬ..እኛጋም ነገሮች ጥሩ ናቸው….ስራዬንም ወደቤት አዘዋውሬ አንተ ቢሮ ስሰራ ነው ምውለው››
‹‹አንዳንድ ስራዎችሽን አሁን ለቀጠርሻቸው ረዳቶችሽ መስጠት አልቻልሽም?››ሲሉ ጠየቋት፡፡
ስለ ሎዛ እስካሁን አልነገረቻቸውም። አሁን በትከሻቸው ላይ ምንም ተጨማሪ ሸክም ልትጭንባቸው አልፈለገችም።
‹‹አባዬ ስራውን ለሌሎች ለማከፋል እየሞከርኩ ነው..ቢሆንም ታውቃለህ አመታዊው የገቢ ማሰባሰቢያ በአላችን እየደረሰ ነው..በዚህ ጊዜ ስራ ይበዛብናል›› አለች.፡፡
‹‹በዛ ላይ እህትሽን መንከባከቡ በጣም ፈታኝ ስራ ነው››
‹‹ኖ…ኖ አባዬ….አሁን ከእህቴ ጋር በጣም እየተግባባን ስለሆነ ነገሮች የምታስበውን ያህል ከባድ አይደሉም…እናንተ ምንም አታስቡ››
‹‹ይሁን ልጄ…በጣም ነው የምኮራብሽ››
‹‹አመሰግናለው አባዬ…ለመሆኑ ዶክተሮቹ እናቴ ከሆስፒታል መች ትወጣለች ብለው ያስባሉ?››
‹‹ግምቱን አሻሽለዋል፤ከአሁን በኋላ ቢያንስ ሁለት ሳምንት ሳያቆዬት አይቀርም፡፡ ከፀጋ ጋር መነጋገር እችል ይሆን?››
‹‹ይቅርታ አባዬ አሁን ተኝታለች ››
.የእለቱ ተግባራቸውን ሁሉ አከናውነው ወደ ቤት እስኪመጡ ድረስ የፀጋ ባህሪ ከንጭንጭ የራቀና በፈገግታ የተሞላ ሆኖ በመታየቱ አመስጋኝ ነበረች። ግን ወደቤት ከተመለሱ በኃላ መነጫነጭ ጀመረች ከዛ ሰውነቷን አጥባ እራቷን ካበላቻት በኋላ አልጋ ላይ አስቀመጠቻት… ከዛ ትንሿ ልጅ በሰከንዶች ውስጥ ተኛች። ይህም ራሄል ምስኪኗን ልጅ ከወዲህ ወዲያ እያሽከረከረች ስታንገላታት ስለዋለች የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማት አድርጎታል።..እና አሁን ልትቀሰቅሳትና የበለጠ ልታበሳጫት አልፈለገችም፡፡
አባቷን ለተጨማሪ ጥቂት ደቂቃዎች አወራቻቸው፣ አባቷን ስትናገር እንኳን ስራዋ እያንገበገበባት ነበር ..ትኩረቷን የሚከፋፍልባት ምንም ነገር ባይኖር ደስተኛ ነች ።ወዲያው ሌላ ስልክ ተደወለላት.. ቃተተች እና ማን እንደሚደውል ሳታረጋግጥ አነሳችው..ቁጣ በሚመስል የድምፅ ቃና ‹‹ራሄል ነኝ.››አለች
‹‹ሄይ ራሄል… እንዴት ነሽ?››ዔሊያስ ነበር…ፍስስ የሚለውን ድምፁን ስትሰማ ብስጭቷን አቃለላት። ራሄል ዛሬ ወደቤት ከተመለሰች በኋላ ዔሊን ለማየት ፈልጋ ከአሁን አሁን በራፉን ያንኳኳል እያለች በናፍቆት ስትጠብቅነበር፡፡
‹‹ስልክሽ ለረጅም ጊዜ ተይዞ ነበር››
‹‹ከአባቴ ጋር እያወራው ነበር ››አለችው።
‹‹ነገሮች እዛ እንዴት እየሄዱ ነው…?ሄጄ ካየዋቸው እኮ ሳምንት ሊያልፈኝ ነው››
‹‹እናቴ ጥሩ እያገገመች ነው። ግን እስከሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ወደ ቤት እንደማትመጣ ነው የሰማሁት››
‹‹አይዞሽ…ዋናው የመዳን ሂደታችው እድገት እያሳየ መሄዱ ነው››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ታዲያ አሁን ምን እያደረክ ነው? ››ብላ ጠየቀችው
‹‹ምንም…ሶፋዬ ላይ ጋደም ብዬ ስለአንቺና ስለፀጋ እያሰብኩ ነበር››አላት፡፡
ደስ አላት‹‹እየፎገርክ ነው?››
‹‹አረ እውነቴን ነው…መቼስ ማል አትይኝም››
‹‹መምጣት ትፈልጋለህ?›› ቃላቶቹ ድንገት ነው ከአንደበቷ ያመለጧት….የአእምሯዋን ሳይሆን የልቧን ምኞት ነው አንደበቷ ያሳበቀባት….
‹‹ከስራ ከወጣው በኋላ ከሶስት ጊዜ በላይ ልመጣ ተነስቼ ነበር ከዛ ‹‹አረ ኤልያስ እግርና አብዝተሀል…..ሰዎቹን እያጨናነቅካቸው እንዳይሆን ››ብዬ ራሴን በመገሰፅ ያቆምኩት፡፡
‹‹እባክህ ና:: እዚያ ባገኝህ ደስ ኀይለኛል።›› ድጋሚ አመለጣት…በራሷ ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹እንዲህ ከሆነ››አለ ዔሊ በፈገግታ ‹‹ መምጣት የምችል ይመስለኛል….››
‹‹ቆንጆ እራት ሰርቼ ጠብቅሀለው››
‹‹በጣም ደስ የሚል ነገር ነው..በዛውም የሞያ ብቃትሽ ይፈተሻል››
‹‹አንተ የእማዬ ልጅ እኮ ነኝ..በሞያዬማ ምንም ጥርጣሬ ሊገባህ አይገባም››
‹‹እኮ ላየው አይደል?››
‹‹አይ ዛሬ እንኳን አታየውም…ይሄንን ዙሪያዬን የተቆለለ ወረቀት ባለበት ጥዬ ኪችን አልገባም››
‹‹እና እራቱ የለም እያልሺኝ ነው?››
‹‹እሱማ አለ ..ግን አለም ነች የምትሰራው››
‹‹ይሁን እሺ…..እስክንገናኝ ቻው››
‹‹ቻው››ስልኩን ዘጋች፡፡እንደገና ዘና ያለ ስሜት ተሰማት ፡፡
አለምን ተጣራችን እንግዳ ስለሚመጣ ቆንጆ እራት እንድታዘጋጅ አዘዘቻት እና ትኩረት ሰበሰበች እና ወደ ስራዋ ተመለሰች፡፡
///
ረዳቷ ሮቤል ወደእነ ራሄል ቤት መጥቶ አባቷ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ስለፋውንዴሽኑ አመታዊ የገቢ ማሰባሰ
ቢያ ዝግጅት እየተወያዩ ነው፡፡
‹‹የትኛውን ስራ በማን እንደማሰራ እና …የተወሰኑ ስራዎችን ውክልና መስጠት ከየት እንደምጀምር አላውቅም።››ራሄል በንዴት ተነፈሰች።
‹‹ እኔም ስለእሱ እያሰብኩነበር…ሁሉንምነገር በራስሽ ለመስራት በመሞከር በራስሽ ላይ አላስፈላጊ ጫና ማሳደር የለብሽም…እኔ አለሁ››
‹‹እኔ ካንተ የበለጠ ጊዜ አለኝ ብዬ አስባለሁ… ።››
ሮቤል ንግግሯ አልተዋጠለትም፡፡ቢሆንም ብዕሩን በፋይሉ ላይ ሰክቶ እያዳመጣት ነው፡፡በሁሉም ነገር ትዕግስት እያጣ እንደመጣ በሁኔታው መታዘብ ይቻላል፡፡
‹‹ራሄል እህትሽን በመንከባከብ እንደተጠመድሽ አውቃለሁ…የደከመሽ ትመስላያለሽ ።አሁን የሎዛን ስራ የሚሰራ ሌላ ሰው መፈለግ አለብሽ እና ጊዜ እንደሌለሽ አውቃለሁ። ››በማለት የሚያስበውን በግልፅ ነገራት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰተ_በዘሪሁን_ገመቹ
___
//
ዛሬ ጠዋት ሎዛን ከስራ መባረሯን ለመናገር ፀጋን ይዛ ወደ ፋውንዴሽን ቢሮ ሄዳ ነበር፡፡
የሎዛ ክህደት አሁንም እያመማት ነው፣እሷን በመገላገሏ ደስ ብትሰኝም ከእስከአሁኑ በባሰ ሁኔታ፣ የስራ ጫናው ሊጠነክርባት እንደሚችል ተሰምቷታል።እሷ የምትፈልገውን ስራ በእቅዳቸው መሰረት እንዲከወንላት ከፈለገች ሁለት ተጨማሪ ጥንድ እጆች፣ አይኖች እና ጆሮዎች ያስፈልጋታል።
ራሄል በቁጭት እና በንዴት ቢሮ ቁጭ ብላ ከሮቤል ጋር እያወራች ነው፡፡
‹‹ ሮቤል በሆነው ነገር በጣም አዝኛለው…የማፍያ ፀባይ ካላቸው የበጎ አድራጎት ድርጅተች ጋር ተመሳጥራ በእኔ ድርጅት ስም ልትዘረፍ ስትል ነው የያዝኳት››
‹‹አዎ..ከዚህ በፊት የምታደርጋቸው አንዳንድ ሁኔተዎች ሳላላማሩኝ ጥንቀቄ እንድታደርጊ ጠቆም አድርጌሽ ነበረ….ይመስለኛል እንደቁምነገር ወስደሸሽ አላዳመጥሽኝም››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…በጣም እኮ ነበር የማምናት››
‹‹ለማንኛውም ከፍተኛ ኪሳራ ሳታስከትል በጊዜ ስለደረሽባት ጥሩ ነገር ነው….ለወደፊቱ ትምህርት ይሆንሻል››አላት፡፡
‹‹ አዎ ትክክል ነህ…ለማንኛውም አሁን ሌላ ጎበዝ እና ታማኝ ረዳት ማግኘት አለብኝ ፡፡››
‹‹ያንን ስራ በንዑስ ኮንትራት ማሰራት የሚሻል ይመስለኛል››የሚል ምክር ሰጣት፡፡
‹‹አይ ይህ በራሴ ማድረግ አለብኝ።ብቻ በፋውንዴሽኑ ላይ ሌላ ጉዳት እንዳላደረሰች ተስፋ አደርጋለሁ።››
የቢሮውን ስራ ለሮቤል በአደራ ሰጥታ ፀጋን ይዛ ከቢሮ ወጣችና ወደሆስፒታል ነው የሄደችው፡፡ፀጋ ታማ ሳይሆን መደበኛ ክትትል የምታደርግባትን ቀን ስለሆነ ነበር ወደ ሆስፒታል የወሰደቻት..ከዛ በኋላ ነው ወደቤታቸው የተመለሱት፡፡
ራሄል በምትወደው ሶፋ ላይ ተቀምጣ ትራስ በመደግፋ ወረቀቶች እያገላበጠች ሳለ ስልኳ ጠራ..አነሳችና አየችው፡፡አባቷ ናቸው፡፡በጭኗ ላይ ያሉትን ወረቀቶች ማገለባበጧን ሳታቆም አባቷን ማውራት ጀመረች፡፡
‹‹አባዬ እንዴት ነህ..እማዬስ?››
‹‹እናትሽ በጣም ቆራጥ ነች እና ዶክተሮቹ በጤናዋ መሻሻል በጣም ተደስተዋል.››አላት አባቷ፡፡
‹‹ደስ ብሎኛል አባዬ..እኛጋም ነገሮች ጥሩ ናቸው….ስራዬንም ወደቤት አዘዋውሬ አንተ ቢሮ ስሰራ ነው ምውለው››
‹‹አንዳንድ ስራዎችሽን አሁን ለቀጠርሻቸው ረዳቶችሽ መስጠት አልቻልሽም?››ሲሉ ጠየቋት፡፡
ስለ ሎዛ እስካሁን አልነገረቻቸውም። አሁን በትከሻቸው ላይ ምንም ተጨማሪ ሸክም ልትጭንባቸው አልፈለገችም።
‹‹አባዬ ስራውን ለሌሎች ለማከፋል እየሞከርኩ ነው..ቢሆንም ታውቃለህ አመታዊው የገቢ ማሰባሰቢያ በአላችን እየደረሰ ነው..በዚህ ጊዜ ስራ ይበዛብናል›› አለች.፡፡
‹‹በዛ ላይ እህትሽን መንከባከቡ በጣም ፈታኝ ስራ ነው››
‹‹ኖ…ኖ አባዬ….አሁን ከእህቴ ጋር በጣም እየተግባባን ስለሆነ ነገሮች የምታስበውን ያህል ከባድ አይደሉም…እናንተ ምንም አታስቡ››
‹‹ይሁን ልጄ…በጣም ነው የምኮራብሽ››
‹‹አመሰግናለው አባዬ…ለመሆኑ ዶክተሮቹ እናቴ ከሆስፒታል መች ትወጣለች ብለው ያስባሉ?››
‹‹ግምቱን አሻሽለዋል፤ከአሁን በኋላ ቢያንስ ሁለት ሳምንት ሳያቆዬት አይቀርም፡፡ ከፀጋ ጋር መነጋገር እችል ይሆን?››
‹‹ይቅርታ አባዬ አሁን ተኝታለች ››
.የእለቱ ተግባራቸውን ሁሉ አከናውነው ወደ ቤት እስኪመጡ ድረስ የፀጋ ባህሪ ከንጭንጭ የራቀና በፈገግታ የተሞላ ሆኖ በመታየቱ አመስጋኝ ነበረች። ግን ወደቤት ከተመለሱ በኃላ መነጫነጭ ጀመረች ከዛ ሰውነቷን አጥባ እራቷን ካበላቻት በኋላ አልጋ ላይ አስቀመጠቻት… ከዛ ትንሿ ልጅ በሰከንዶች ውስጥ ተኛች። ይህም ራሄል ምስኪኗን ልጅ ከወዲህ ወዲያ እያሽከረከረች ስታንገላታት ስለዋለች የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማት አድርጎታል።..እና አሁን ልትቀሰቅሳትና የበለጠ ልታበሳጫት አልፈለገችም፡፡
አባቷን ለተጨማሪ ጥቂት ደቂቃዎች አወራቻቸው፣ አባቷን ስትናገር እንኳን ስራዋ እያንገበገበባት ነበር ..ትኩረቷን የሚከፋፍልባት ምንም ነገር ባይኖር ደስተኛ ነች ።ወዲያው ሌላ ስልክ ተደወለላት.. ቃተተች እና ማን እንደሚደውል ሳታረጋግጥ አነሳችው..ቁጣ በሚመስል የድምፅ ቃና ‹‹ራሄል ነኝ.››አለች
‹‹ሄይ ራሄል… እንዴት ነሽ?››ዔሊያስ ነበር…ፍስስ የሚለውን ድምፁን ስትሰማ ብስጭቷን አቃለላት። ራሄል ዛሬ ወደቤት ከተመለሰች በኋላ ዔሊን ለማየት ፈልጋ ከአሁን አሁን በራፉን ያንኳኳል እያለች በናፍቆት ስትጠብቅነበር፡፡
‹‹ስልክሽ ለረጅም ጊዜ ተይዞ ነበር››
‹‹ከአባቴ ጋር እያወራው ነበር ››አለችው።
‹‹ነገሮች እዛ እንዴት እየሄዱ ነው…?ሄጄ ካየዋቸው እኮ ሳምንት ሊያልፈኝ ነው››
‹‹እናቴ ጥሩ እያገገመች ነው። ግን እስከሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ወደ ቤት እንደማትመጣ ነው የሰማሁት››
‹‹አይዞሽ…ዋናው የመዳን ሂደታችው እድገት እያሳየ መሄዱ ነው››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ታዲያ አሁን ምን እያደረክ ነው? ››ብላ ጠየቀችው
‹‹ምንም…ሶፋዬ ላይ ጋደም ብዬ ስለአንቺና ስለፀጋ እያሰብኩ ነበር››አላት፡፡
ደስ አላት‹‹እየፎገርክ ነው?››
‹‹አረ እውነቴን ነው…መቼስ ማል አትይኝም››
‹‹መምጣት ትፈልጋለህ?›› ቃላቶቹ ድንገት ነው ከአንደበቷ ያመለጧት….የአእምሯዋን ሳይሆን የልቧን ምኞት ነው አንደበቷ ያሳበቀባት….
‹‹ከስራ ከወጣው በኋላ ከሶስት ጊዜ በላይ ልመጣ ተነስቼ ነበር ከዛ ‹‹አረ ኤልያስ እግርና አብዝተሀል…..ሰዎቹን እያጨናነቅካቸው እንዳይሆን ››ብዬ ራሴን በመገሰፅ ያቆምኩት፡፡
‹‹እባክህ ና:: እዚያ ባገኝህ ደስ ኀይለኛል።›› ድጋሚ አመለጣት…በራሷ ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹እንዲህ ከሆነ››አለ ዔሊ በፈገግታ ‹‹ መምጣት የምችል ይመስለኛል….››
‹‹ቆንጆ እራት ሰርቼ ጠብቅሀለው››
‹‹በጣም ደስ የሚል ነገር ነው..በዛውም የሞያ ብቃትሽ ይፈተሻል››
‹‹አንተ የእማዬ ልጅ እኮ ነኝ..በሞያዬማ ምንም ጥርጣሬ ሊገባህ አይገባም››
‹‹እኮ ላየው አይደል?››
‹‹አይ ዛሬ እንኳን አታየውም…ይሄንን ዙሪያዬን የተቆለለ ወረቀት ባለበት ጥዬ ኪችን አልገባም››
‹‹እና እራቱ የለም እያልሺኝ ነው?››
‹‹እሱማ አለ ..ግን አለም ነች የምትሰራው››
‹‹ይሁን እሺ…..እስክንገናኝ ቻው››
‹‹ቻው››ስልኩን ዘጋች፡፡እንደገና ዘና ያለ ስሜት ተሰማት ፡፡
አለምን ተጣራችን እንግዳ ስለሚመጣ ቆንጆ እራት እንድታዘጋጅ አዘዘቻት እና ትኩረት ሰበሰበች እና ወደ ስራዋ ተመለሰች፡፡
///
ረዳቷ ሮቤል ወደእነ ራሄል ቤት መጥቶ አባቷ ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ስለፋውንዴሽኑ አመታዊ የገቢ ማሰባሰ
ቢያ ዝግጅት እየተወያዩ ነው፡፡
‹‹የትኛውን ስራ በማን እንደማሰራ እና …የተወሰኑ ስራዎችን ውክልና መስጠት ከየት እንደምጀምር አላውቅም።››ራሄል በንዴት ተነፈሰች።
‹‹ እኔም ስለእሱ እያሰብኩነበር…ሁሉንምነገር በራስሽ ለመስራት በመሞከር በራስሽ ላይ አላስፈላጊ ጫና ማሳደር የለብሽም…እኔ አለሁ››
‹‹እኔ ካንተ የበለጠ ጊዜ አለኝ ብዬ አስባለሁ… ።››
ሮቤል ንግግሯ አልተዋጠለትም፡፡ቢሆንም ብዕሩን በፋይሉ ላይ ሰክቶ እያዳመጣት ነው፡፡በሁሉም ነገር ትዕግስት እያጣ እንደመጣ በሁኔታው መታዘብ ይቻላል፡፡
‹‹ራሄል እህትሽን በመንከባከብ እንደተጠመድሽ አውቃለሁ…የደከመሽ ትመስላያለሽ ።አሁን የሎዛን ስራ የሚሰራ ሌላ ሰው መፈለግ አለብሽ እና ጊዜ እንደሌለሽ አውቃለሁ። ››በማለት የሚያስበውን በግልፅ ነገራት፡፡
ራሄል ከንፈሯን ነከሰች። ከእሱ ጋር እያወራች ቢሆንም በተመሳሳይ ጊዜ ኮምፒውተሯ ላይ ባለው ፎርም እያስገባች ያለችውን መረጃ ከማስተር ፋይሉ ጋር እያመሳከረች ነው። በየዓመቱ የምታደርገው ዝግጅቱ ምን እንደሚፈልግ በትክክል ታውቃለች ፡፡እናም በየዓመቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚደረገው አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በብዙ ሚዲያዎች ሽፋን የሚያገኝ ..ትላልቅ የሀገሪቱ ሀብታሞችና የጥበብ ሰዎች፤የሀይማኖት ሰዎች እና ባለስልጣናት ከልባቸው አምነውበትም ሆነ ለታይታ ብለው በመጋፋት የሚሳተፉበት፤ ለድርጅቱ አብዛኛው ባጀት የሚሰበሰብበት ትልቅ ዝግጅት ነው. እና እስከዛሬ በነበሩት ዝግጅቶች እያንዳንዱ ጥቃቅን ነገሮች ሳይቀር በእሷ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትና ክትትል የሚከወኑ ነበሩ…ዘንድሮም ምንም እንኳን ፀጋን ከመንከባከብ ጋር እንዴት አንድ ላይ እንደምታስኬደው ባታውቅም…ነገሮች ግን በተመሳሳይ መንገድ እንደሚቀጥሉ እርግጠኛ ነች..ለዛም ብላ ነው የዘንድሮ አመታዊ ዝግጅት ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው በወላጆቾ ግዙፍ መኖሪያ ቤት ግቢ ውስጥ እንዲከናወን ውሳኔ ያስተላለፈችው፡፡ እንደዛ ከሆነ ፀጋን መንከባከብ ሆነ ዝግጅቱን ማቀናጀትን ትወጣዋለች፡፡
ሮቤልን ከእስክሪብቶ ጋር እያደረገ ያለው ጫወታ ጨመረ ..ድፍረቱን አሰባስቦ‹‹ራሄል አሁን መነጋገር ያለብን ይመስለኛል ››አላት….ቃላቶቹ ትኩረቷን ሳቧት።
‹‹አንድ ሰው መነጋገር አለብን ካለ ..ጉዳዩ በጣም ውጥረት ያለበትና ወሳኝ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡
‹‹እየተነጋገርን አይደል…?መናገር የምትፈልገው ነገር ካለ..እያዳመጥኩህ ነው››አለችው፡፡
እጁን ወደጭንቅላቱ ላከና ፀጉሩን አከክ..አከክ እደረገ … ከመቀመጫው ተነሳ..ከዛ ወደእሷ በትኩረት እየተመለከተ‹‹ስራ ስጀምር ቀስ በቀስ የበለጠ ሀላፊነት የሚሰጠኝና ለድርጅቱ ጠቅሜ እራሴንም እያሻሻልኩ የምሄድ መስሎኝ ነበር ። አውቃለው በፋውንዴሽኑ ውስጥ የቆየውት ለስድስት ወራት ብቻ ነው።ቢሆንም ግን በእነዚያ ስድስት ወራት ውስጥ የስራ አካሄዱን እና እኔ ያለኝን ቦታና ተፈላጊነት ብዙም እንዳልተረዳሁ መናዘዝ አለብኝ። ሁሉንም ስራዎች በራስሽ ነው የምትሰሪያቸው። የበለጠ ኃላፊነት ለመረከብ የበለጠ መልፋትና እራሴን ማሳየት እንዳለብኝ አውቃለው….ግን ቢያንስ ወደየት እንደምጓዝ መንገዶቹን ከአሁኑ ማወቅ አለብኝ… እንደዛ ሲሆን ነው ተስፋ ማድረግና መበርታት የምችለው.. ፡፡ እኔ ወጣት ነኝ፣ እድገት በማያሰይ ስራ ላይ ጊዜዬን ማጥፋት የለብኝም ።ነገሩን በስህተት አትይብኝና ..በእውርድንብር ነው እተጓዝኩ ያለሁት፡፡››› አላት፡፡
ራሄል ብልጭ አለባት። ቃላቶቹ ከእሱ በፊት የነበረችው ሰራተኛ ስራ ስታቆም ከተናገረችው ጋር ቀጥተኛ ኮፒ ነው። ሎዛን በክህደቷ ባባረረችበትና የአመታዊ ገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚደረግበት በዚህ ጊዜ ሮቤልን የማጣት አቅም የላትም።ሮቤልን ተመለከተች፣ ትክክለኛውን ነገር መናገር እንድትችል ተመኘች።
ትናንት ከመፅሀፍ ቅዱስ ያነበበችው ‹‹ እኔ ስደክም ያን ጊዜ ብርቱ ነኝና።››የሚለው ቃል ወደ ህሊናዋ መጣ፣ ወደ ልቧ ብርሃን ገባ፣ትኩረቷን ሳበሰበች።
ሮቤል በጣም ተጨንቆ ነበር።ቀና ብላ ተመለከተችው እና ቃላቱ በአእምሮዋ ውስጥ ሲያስተጋባ፣የተናገረው ሁሉ ትክክል እንደሆነ ተገነዘበች፡፡ በረጅሙ ተነፈሰች እና መናገር ጀመረች፡፡
‹‹እሺ ለአንተ ጠቃሚ ስራ አለኝ። ሎዛን የሚተካ ሰራተኛ ፈልግና ቅጠር..ከዛ በኃላ ለአመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አቀናጅ አድርጌ እሾምሃለሁ..ይሄ ለፋውንዴሽኑ የጀርባ አጥንት የሆነ ትልቅ ዝግጅት ሙሉ ኃላፊነት በአንተ ትከሻ ላይ ያርፋል ማለት ነው…ቀጣይ ምን ማድረግ እንደምንችል ደግሞ የዝግጅቱን አፈፃፀም ገምግመን እንወስናለን..››አለችውና ወዲያው የዝግጅቱን እቅዶችን የያዙ ወረቀቶችን ቀጥታ ከኮምፒውተሩ ፕሪንት አድርጋ ተመለከተቻቸው እና ሃሳቧን ከመቀየር በፊት ሰጠችው።
‹‹ይህ እኔ የምጠቀመው ዝርዝር እቅድ ነው ።እንደጋይድ ተጠቅመህ የራስህን ማሻሻያና ፈጠራ ልትጨምርበት ትችላለህ… ጥያቄ ካለህ በማንኛውም ሰዓት አለው››
. ሮቤል በጥልቅ ፈገግታ ወረቀቶቹን ተቀበላትና ገለበጠባቸው።‹‹እሺ ከቀላል እንጀምራለን.፣በጣም አመሰግናለው››አላት፡፡የሀሳብ ልዩነታቸው ካሰበው በተቃራኒው በሰላማዊ መንገድ ስለተፈታ በጣም ደስ አለው፡፡
ከአንድ ሰአት ቆይታ በኋላ ሮቤል እያፏጨ ከቤት ወጣ። ራሄል የቤታቸውን ደረጃ ወርዶና ግቢውን አቆርጦ ወደ መኪናው ሲገባ ተመለከተችው።በፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ በሩቅ ይታያል።‹‹ትክክለኛውን ነገር ነው ያደረኩት ?››እራሷን ጠየቀች፡‹‹አዎ ሮቤል ጎበዝ ሰራተኛ ነው… በችሎታው ከመጠን በላይ ይተማመናል፤በመጠኑ
ነበር የሳሎኑ ደውል ያቃጨለው….‹‹ወይ ሳለባብስ ዓሊ መጣ››አለችና ወረቀቱና በለበት በታትና ወደመኝታ ክፍሏ ሮጠች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ሮቤልን ከእስክሪብቶ ጋር እያደረገ ያለው ጫወታ ጨመረ ..ድፍረቱን አሰባስቦ‹‹ራሄል አሁን መነጋገር ያለብን ይመስለኛል ››አላት….ቃላቶቹ ትኩረቷን ሳቧት።
‹‹አንድ ሰው መነጋገር አለብን ካለ ..ጉዳዩ በጣም ውጥረት ያለበትና ወሳኝ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡
‹‹እየተነጋገርን አይደል…?መናገር የምትፈልገው ነገር ካለ..እያዳመጥኩህ ነው››አለችው፡፡
እጁን ወደጭንቅላቱ ላከና ፀጉሩን አከክ..አከክ እደረገ … ከመቀመጫው ተነሳ..ከዛ ወደእሷ በትኩረት እየተመለከተ‹‹ስራ ስጀምር ቀስ በቀስ የበለጠ ሀላፊነት የሚሰጠኝና ለድርጅቱ ጠቅሜ እራሴንም እያሻሻልኩ የምሄድ መስሎኝ ነበር ። አውቃለው በፋውንዴሽኑ ውስጥ የቆየውት ለስድስት ወራት ብቻ ነው።ቢሆንም ግን በእነዚያ ስድስት ወራት ውስጥ የስራ አካሄዱን እና እኔ ያለኝን ቦታና ተፈላጊነት ብዙም እንዳልተረዳሁ መናዘዝ አለብኝ። ሁሉንም ስራዎች በራስሽ ነው የምትሰሪያቸው። የበለጠ ኃላፊነት ለመረከብ የበለጠ መልፋትና እራሴን ማሳየት እንዳለብኝ አውቃለው….ግን ቢያንስ ወደየት እንደምጓዝ መንገዶቹን ከአሁኑ ማወቅ አለብኝ… እንደዛ ሲሆን ነው ተስፋ ማድረግና መበርታት የምችለው.. ፡፡ እኔ ወጣት ነኝ፣ እድገት በማያሰይ ስራ ላይ ጊዜዬን ማጥፋት የለብኝም ።ነገሩን በስህተት አትይብኝና ..በእውርድንብር ነው እተጓዝኩ ያለሁት፡፡››› አላት፡፡
ራሄል ብልጭ አለባት። ቃላቶቹ ከእሱ በፊት የነበረችው ሰራተኛ ስራ ስታቆም ከተናገረችው ጋር ቀጥተኛ ኮፒ ነው። ሎዛን በክህደቷ ባባረረችበትና የአመታዊ ገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚደረግበት በዚህ ጊዜ ሮቤልን የማጣት አቅም የላትም።ሮቤልን ተመለከተች፣ ትክክለኛውን ነገር መናገር እንድትችል ተመኘች።
ትናንት ከመፅሀፍ ቅዱስ ያነበበችው ‹‹ እኔ ስደክም ያን ጊዜ ብርቱ ነኝና።››የሚለው ቃል ወደ ህሊናዋ መጣ፣ ወደ ልቧ ብርሃን ገባ፣ትኩረቷን ሳበሰበች።
ሮቤል በጣም ተጨንቆ ነበር።ቀና ብላ ተመለከተችው እና ቃላቱ በአእምሮዋ ውስጥ ሲያስተጋባ፣የተናገረው ሁሉ ትክክል እንደሆነ ተገነዘበች፡፡ በረጅሙ ተነፈሰች እና መናገር ጀመረች፡፡
‹‹እሺ ለአንተ ጠቃሚ ስራ አለኝ። ሎዛን የሚተካ ሰራተኛ ፈልግና ቅጠር..ከዛ በኃላ ለአመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አቀናጅ አድርጌ እሾምሃለሁ..ይሄ ለፋውንዴሽኑ የጀርባ አጥንት የሆነ ትልቅ ዝግጅት ሙሉ ኃላፊነት በአንተ ትከሻ ላይ ያርፋል ማለት ነው…ቀጣይ ምን ማድረግ እንደምንችል ደግሞ የዝግጅቱን አፈፃፀም ገምግመን እንወስናለን..››አለችውና ወዲያው የዝግጅቱን እቅዶችን የያዙ ወረቀቶችን ቀጥታ ከኮምፒውተሩ ፕሪንት አድርጋ ተመለከተቻቸው እና ሃሳቧን ከመቀየር በፊት ሰጠችው።
‹‹ይህ እኔ የምጠቀመው ዝርዝር እቅድ ነው ።እንደጋይድ ተጠቅመህ የራስህን ማሻሻያና ፈጠራ ልትጨምርበት ትችላለህ… ጥያቄ ካለህ በማንኛውም ሰዓት አለው››
. ሮቤል በጥልቅ ፈገግታ ወረቀቶቹን ተቀበላትና ገለበጠባቸው።‹‹እሺ ከቀላል እንጀምራለን.፣በጣም አመሰግናለው››አላት፡፡የሀሳብ ልዩነታቸው ካሰበው በተቃራኒው በሰላማዊ መንገድ ስለተፈታ በጣም ደስ አለው፡፡
ከአንድ ሰአት ቆይታ በኋላ ሮቤል እያፏጨ ከቤት ወጣ። ራሄል የቤታቸውን ደረጃ ወርዶና ግቢውን አቆርጦ ወደ መኪናው ሲገባ ተመለከተችው።በፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ በሩቅ ይታያል።‹‹ትክክለኛውን ነገር ነው ያደረኩት ?››እራሷን ጠየቀች፡‹‹አዎ ሮቤል ጎበዝ ሰራተኛ ነው… በችሎታው ከመጠን በላይ ይተማመናል፤በመጠኑ
ነበር የሳሎኑ ደውል ያቃጨለው….‹‹ወይ ሳለባብስ ዓሊ መጣ››አለችና ወረቀቱና በለበት በታትና ወደመኝታ ክፍሏ ሮጠች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
የግዜርየአደራልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ከብዙ ድካምና ልፋት በኃላ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባበሰቢያ ቀን ደረሰ፡፡አሁን በግዙፉ እና ነፋሻማው በወላጆቿ ቤት ሁሉም አይነት ዝግጅት ተጠናቆ እንግዶችን በመጠባበቅ ላይ ናቸው‹‹እርግጠኛ ነህ ምንም ነገር የጎደለ የለም?›› ራሔል ሮቤልን ለአራተኛ ጊዜ ጠየቀችው።
በሙሉ የራስ መተማመን‹‹ሁሉ ነገር በቁጥጥር ስር ነው…አንቺ ምንም አታስቢ›› ሲል መለሰላት፡፡
ራሄል የመጀመሪያ እንግዶች በእርሻ ቦታው ላይ በሰዓቱ ሲደርሱ ስትመለከት ተደሰተች። እሷ እንደዚህ ቀደሞቹ ዝግጅቶች ሙሉ ቁጥጥር አልነበራትም። በዚህም ምክንያት በሁሉ ነገር ላይ በቀላሉ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡
በነገራት ነገር እንዳላመነችው የተረዳው ሮቤል‹‹ ደህና ነን። ነገሮች ጥሩ ናቸው። ሁሉም ሰው በጥሩ ሁኔታ ስራውን እየሰራ ነው። ምንም አትጨናነቂ ዘና በይ … ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች ገንዘብ መሰብሰብ ሲጀመር የፋውንዴሽናችን ካዝና ሞልቶ ይፈሳል፡፡ ››አላት፡፡
ከመጠን ያለፈ በራስ መተማመኑን አልወደደችለትም፡፡ቢሆንም ማድረግ የምትችለው ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ያልታሰብ ችግር እንዳይፈጠር መፀለይ ብቻ ነው፡፡ግን ችግሩ መፀለዩም ለእሷ በቀላሉ መደረግ የሚቻል ነገር አይደለም፡፡
ቀስ በቀስ ግቢው በእንግዶች እየተሞላ መጣ…የቅርቧ ሰዎች ጓደኞቾና ዘመዶቾን ጨምሮ ከዚህ በፊት በዝግጅቷቾ ላይ ተገኝተው የማያውቁ ሚዲያ ብቻ ማታውቃቸው በርካታ ታዋቂ እና ዝነኛ ሰዎች እዚህምእዛም ስታይ በጣም ተገረመች…የሚዲያ ሰዎች በየቦታው እየተሹለከለኩ የመረጡትን ሰው ፎቶ በማነሳትና ቃለመጠየው በማድረግ ተጠምደዋል፡፡
የሚገርም ሁኔታ ቀስ በቀስ የበለጠ ነፃነት፣ እና ቀላል ያለ ስሜት እየተሰማት መጣ።ስሯ ያለችው ፀጋ እጇን ስትይዛት ወደቀልቧ ተመለሰች እና ወደታች አጎንብሳ ተመለከተቻት።
በጣቷ ወደ ግራ እየጠቆመቻት‹‹ኤሊ..ኤሊ››አለቻት፡፡ራሄል ጥቆማዋን ተከትላ እይታዋን ወደዛው አዞረች፡፡ዶ/ር ኤልያስ ወደእነሱ እየመጣ ነው፡፡ጥቁር ሙሉ ሱፍ ለብሶ ሽክ ብሏል፡፡ስራቸው ሲደርስ
‹‹ኤሊ. ኤሊ. መጣህ››ትሁት ጮኸች.
የራሄል ልብ ዘለለ፡፡ ዔሊያስ ጎንበስ ብሎ ፀጋን በእቅፉ አስገባትና ስሞ መልሷ አስቀመጣት…። በዚህ ጊዜ ሮቤል ራሄል ጀርባ ደርሶ የሁነ ነገር በሹክሹክታ እየነገራት ነበር፡፡
የኤልያስ የደመቁ ጥቁር ዓይኖቹ ወደ ሮቤል በረሩ፣ ‹‹ኤሊ ሮቤል ይባላል … ረዳቴ ነው .››ብላ አስተዋወቀችው፡፡
‹‹ሮቤል እሱ ደግሞ ዶ/ር ኤልያስ ይባላል…››በቀደም ከንፈሬን የሳመኝ እሱ ነው› የሚለውን ተጨማሪ ንግግር በውስጧ አከለችበት ,፡፡
ዔሊያስ የሮቤልን እጅ እየጨበጠው‹‹ስለተገናኘን ደስ ብሎኛል።››አለው፡፡
ሮቤል በደማቅ ፈገግታ ተሞልቶ በቀልድ መልክ ››ራሔል ስራዎቾን በውክልና ለእኛ አሳላፋ መስጠት እየተማረች ነው። በተቻለህ መጠን ከእኛ አርቀህ ብትይዝልን ደግሞ ነገሮች ከዚህ በላይ እየተሻሻሉ ይሄዳሉ ››አለው
ኤልያስ የሮቤልን ንግግር እያዳመጠ ዓይኖቹ ራሔል ላይ ተከለ።
‹‹እንዳልከው አደርጋለው.››አለው ዔሊያስ…ሮቤል ተሰናብቶቸው ወደስራው ተመለሰ፡፡
ብቻቸውን ሲሆኑ ራሄል ቀሚሷን ወደታች እየጎተተች ያስቸገረቻትን ፀጋን ወደላይ አንስታ አቀፈቻት እና‹‹በመምጣትህ ደስ ብሎኛል››አለችው ።
‹‹አመሰግናለው››አላት
ፀጋ ፀጉሮሯን እየነጨችና ፊቷን እየቧጨረች አስቸገረቻት‹‹አንቺ ሞኝ ልጅ ..እረፊ… ፀጉሬን ነቀልሽው እኮ››አለቻት ራሄል ።
ፀጋ በደስታ ሳቀች ።
‹‹አውርጂኝ ›› ብላ ጠየቀች እና ዔሊያስም እንድታወርዳት ነገራት።እንዳወረደቻት ለመጫወት ከእነሱ ራቅ ብላ ወደ ሜዳው ኩስ ኩስ እያለች ሄደች፡፡
ራሄል ፀጋ የበታተነችባትን ፀጉር ለማስተካከል እየሞከረች ‹‹መጀመሪያ ወደ ቤት ሄጄ ፀጉሬን መልሼ መስራት አለብኝ›› አለችው፡፡
ዔሊያስ ከፀጉሯ ላይ ያረፈች ሳር እያነሳ ‹‹ባታስተካክይውም ቆንጆ ነሽ ››አላት፡፡
ጉንጯ በእፍረት ቀላ‹‹ አመሰግናለው..ግን እንደምታየው ልብሴንም መቀየር አለብኝ?››
ራሄል አለባበሷ ለስራ ከምትለብሰው ልብስ ጋር ሲነፃፀር የተለመደ ነው ግን ሰሞኑን እቤት ስትውል ከምትለብሳቸው ልብሰች አንፃር በጣም ያጌጠና ያመረ የሚባል ነው፡፡
የዔሊያስ ተንኮል አዘል ፈገግታ ተፈታተናት፣ እጁ ዘንበል ብሎ አገጯን እየነካካ ‹‹ጸጉርሽን እንዲህ ስትለቂው ደስ ይለኛል.››ሲላት ለአፍታ ልብን የሚያቆም ፍርሀት ወረራት፡፡
‹‹እንደገና ሊስማኝ ነው እንዴ?›› ብላ በውስጧ አሰበች። እንዲያደርገው ፈለገች።
ፍርሀቷን በሳቅ ለመሸፈን እየጣረች ‹‹ፀጋ ሳትርቅ ብንሄድ ይሻለናል››አለችው፡፡
ወደፀጋ ሄዱና እያንዳንዳቸው አንዳንድ እጃን ያዙ. ራሄል ከሩቅ ለሚያያቸው ሰው ልክ ወደ ወ.ሮ ላምሮት ቤት ሲሄድ እንደነበሩት ቀን ቤተሰብ እንደሚመስሉ አሰበች። ።ወደጎን ዞር ብላ ስታየው ዓይናቸው ተገናኘ። ቢፌ በተደረደረበት ግዙፍ ጠረጴዛ አጠገብ ሲያልፉ የ ሰላጣ ሳህኖች ባዶ ሆነው አየችና እንደመበሳጨት ብላ‹‹ይቅርታ አድርግልኝ..ይህን ማስተካከል አለብኝ.››አለችውና ተለይታቸው ልትሄድ ስትል ዔሊያስ ፈጠን አለና እጇን በእጁ ያዘ።
‹‹አይ, ይሄ የአንቺ ስራ አይደለም, ሮቤል እና አዲሷ ረዳትሽ ሁሉንም ነገር በቁጥጥራቸው ስር አድርገውታል…ለእነሱ ተይላቸው.››አላት፡፡ራሄል ፊቷን አኮሰታተረች እና ተቃውሞዋን ልታሰማ ስትል አንዲት ተለቅ ያለች ነጭ ዩኒፎርም የለበሰች ሴት በላስቲክ የተሸፈነ ሳህን ይዛ መጣችና ባዶውን የሰላጣ ሳህን ስትሞለ ተመለከተች፡፡
ኤሊያስ ቅንድቡን ከፍ አድርጎ ‹‹አየሽ…ዘና በይ ..ሁሉ ነገር አሪፍ ይሆናል?››ሲል ተናገረ።ራሄል በራሷ ችኮነት አፍራ ሳቀች።
‹‹እሺ በቃ ዘና እላለሁ ።››አለችና ረዥሙ ትንፋሽ ሳበች ፣ ዙሪያውን ተመለከተች እና ይህንን እንደምትለምድ ተገነዘበች። የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቱ ብዙ ጊዜ የተጣደፈ ፣ የተቸኮለ ነበር፣አሁን የምታው ግን የተረጋጋ እና ዘና ያለ ሆኖ ነው ያገኘችው ፡፡አሁንም እየፈገገ ያለውን ዔሊን ተመለከተች እና ከሰዎች ጋር በቀላሉ መዋሀድ መቻል እንዴት ጥሩ እንደሆነ አሰበች። ዔሊም እያንዳንዱን እንግዳ ስታናግር ከጎኗ እንዲሆን ፈለገች።
ራሄል በሳቅ ፈገግታ ተጥለቅልቃ‹‹አስደናቂ ቀን ይሆናል ብዬ አስባለሁ››አለችው ።
ኤልያስም‹‹እንደዛ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ ።››ሲል ተጨማሪ ጥንካሬ ሰጣት።ከዚያም ራሄል ይቅርታ ጠየቀችውና አዲስ ወደገቡት እንግዶች ሄደች፡፡እሱ ፀጋን እንደያዘ በተወሰነ ርቀት ወደኃላ ቀረ፡፡ እንግዶቹን እያወራች ትኩረቷ በዔሊ ላይ ነበር።
ኤልያስ ዙሪያ ገባውን እየቃኘ የራሱን ትዝብት መውሰድ ጀመረ…አዎ እሱም እንደማንኛውም ሰው የራሱ እቅድ ነበረው፣ ነገር ግን ከዚህ ህዝብ ጋር ለመስማማት ትንሽ ከፍ ብሎ ማቀድ፣ ትንሽ መስራት፣ የአምስት አመት እቅድን ቢያንስ ወደ አስር አመት ማስፋፋት ይኖርበታል።እና የዛን ጊዜ በእንደዚህ አይነት ዝግጅት ላይ ከሚሳተፉ ከላይኛው ማህበረሰብ ሰዎች ጋር በደንብ ተቀላቅሎ ዘና ብሎ ማውራት ይችል ይሆናል..እስከዛው ግን እንደተነጠለ መቆየት መርጧል፡፡
በሀሳብ ተውጦ ሳለ ድንገት ከኋላው መጣችና‹‹ሰላም ነህ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ደህና ነኝ። ትንሽ የመጨናነቅ ስሜት እየተሰማኝ ነው።›› ሲል መለሰላት፡፡
‹‹ብዙ አዲስ ፊቶች ሲመጡ እያየው ነው›› አለች ራሄል ። ‹‹ግን ከጊዜ በኋላ ታውቋቸዋለህ። ››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ከብዙ ድካምና ልፋት በኃላ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባበሰቢያ ቀን ደረሰ፡፡አሁን በግዙፉ እና ነፋሻማው በወላጆቿ ቤት ሁሉም አይነት ዝግጅት ተጠናቆ እንግዶችን በመጠባበቅ ላይ ናቸው‹‹እርግጠኛ ነህ ምንም ነገር የጎደለ የለም?›› ራሔል ሮቤልን ለአራተኛ ጊዜ ጠየቀችው።
በሙሉ የራስ መተማመን‹‹ሁሉ ነገር በቁጥጥር ስር ነው…አንቺ ምንም አታስቢ›› ሲል መለሰላት፡፡
ራሄል የመጀመሪያ እንግዶች በእርሻ ቦታው ላይ በሰዓቱ ሲደርሱ ስትመለከት ተደሰተች። እሷ እንደዚህ ቀደሞቹ ዝግጅቶች ሙሉ ቁጥጥር አልነበራትም። በዚህም ምክንያት በሁሉ ነገር ላይ በቀላሉ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡
በነገራት ነገር እንዳላመነችው የተረዳው ሮቤል‹‹ ደህና ነን። ነገሮች ጥሩ ናቸው። ሁሉም ሰው በጥሩ ሁኔታ ስራውን እየሰራ ነው። ምንም አትጨናነቂ ዘና በይ … ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች ገንዘብ መሰብሰብ ሲጀመር የፋውንዴሽናችን ካዝና ሞልቶ ይፈሳል፡፡ ››አላት፡፡
ከመጠን ያለፈ በራስ መተማመኑን አልወደደችለትም፡፡ቢሆንም ማድረግ የምትችለው ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ያልታሰብ ችግር እንዳይፈጠር መፀለይ ብቻ ነው፡፡ግን ችግሩ መፀለዩም ለእሷ በቀላሉ መደረግ የሚቻል ነገር አይደለም፡፡
ቀስ በቀስ ግቢው በእንግዶች እየተሞላ መጣ…የቅርቧ ሰዎች ጓደኞቾና ዘመዶቾን ጨምሮ ከዚህ በፊት በዝግጅቷቾ ላይ ተገኝተው የማያውቁ ሚዲያ ብቻ ማታውቃቸው በርካታ ታዋቂ እና ዝነኛ ሰዎች እዚህምእዛም ስታይ በጣም ተገረመች…የሚዲያ ሰዎች በየቦታው እየተሹለከለኩ የመረጡትን ሰው ፎቶ በማነሳትና ቃለመጠየው በማድረግ ተጠምደዋል፡፡
የሚገርም ሁኔታ ቀስ በቀስ የበለጠ ነፃነት፣ እና ቀላል ያለ ስሜት እየተሰማት መጣ።ስሯ ያለችው ፀጋ እጇን ስትይዛት ወደቀልቧ ተመለሰች እና ወደታች አጎንብሳ ተመለከተቻት።
በጣቷ ወደ ግራ እየጠቆመቻት‹‹ኤሊ..ኤሊ››አለቻት፡፡ራሄል ጥቆማዋን ተከትላ እይታዋን ወደዛው አዞረች፡፡ዶ/ር ኤልያስ ወደእነሱ እየመጣ ነው፡፡ጥቁር ሙሉ ሱፍ ለብሶ ሽክ ብሏል፡፡ስራቸው ሲደርስ
‹‹ኤሊ. ኤሊ. መጣህ››ትሁት ጮኸች.
የራሄል ልብ ዘለለ፡፡ ዔሊያስ ጎንበስ ብሎ ፀጋን በእቅፉ አስገባትና ስሞ መልሷ አስቀመጣት…። በዚህ ጊዜ ሮቤል ራሄል ጀርባ ደርሶ የሁነ ነገር በሹክሹክታ እየነገራት ነበር፡፡
የኤልያስ የደመቁ ጥቁር ዓይኖቹ ወደ ሮቤል በረሩ፣ ‹‹ኤሊ ሮቤል ይባላል … ረዳቴ ነው .››ብላ አስተዋወቀችው፡፡
‹‹ሮቤል እሱ ደግሞ ዶ/ር ኤልያስ ይባላል…››በቀደም ከንፈሬን የሳመኝ እሱ ነው› የሚለውን ተጨማሪ ንግግር በውስጧ አከለችበት ,፡፡
ዔሊያስ የሮቤልን እጅ እየጨበጠው‹‹ስለተገናኘን ደስ ብሎኛል።››አለው፡፡
ሮቤል በደማቅ ፈገግታ ተሞልቶ በቀልድ መልክ ››ራሔል ስራዎቾን በውክልና ለእኛ አሳላፋ መስጠት እየተማረች ነው። በተቻለህ መጠን ከእኛ አርቀህ ብትይዝልን ደግሞ ነገሮች ከዚህ በላይ እየተሻሻሉ ይሄዳሉ ››አለው
ኤልያስ የሮቤልን ንግግር እያዳመጠ ዓይኖቹ ራሔል ላይ ተከለ።
‹‹እንዳልከው አደርጋለው.››አለው ዔሊያስ…ሮቤል ተሰናብቶቸው ወደስራው ተመለሰ፡፡
ብቻቸውን ሲሆኑ ራሄል ቀሚሷን ወደታች እየጎተተች ያስቸገረቻትን ፀጋን ወደላይ አንስታ አቀፈቻት እና‹‹በመምጣትህ ደስ ብሎኛል››አለችው ።
‹‹አመሰግናለው››አላት
ፀጋ ፀጉሮሯን እየነጨችና ፊቷን እየቧጨረች አስቸገረቻት‹‹አንቺ ሞኝ ልጅ ..እረፊ… ፀጉሬን ነቀልሽው እኮ››አለቻት ራሄል ።
ፀጋ በደስታ ሳቀች ።
‹‹አውርጂኝ ›› ብላ ጠየቀች እና ዔሊያስም እንድታወርዳት ነገራት።እንዳወረደቻት ለመጫወት ከእነሱ ራቅ ብላ ወደ ሜዳው ኩስ ኩስ እያለች ሄደች፡፡
ራሄል ፀጋ የበታተነችባትን ፀጉር ለማስተካከል እየሞከረች ‹‹መጀመሪያ ወደ ቤት ሄጄ ፀጉሬን መልሼ መስራት አለብኝ›› አለችው፡፡
ዔሊያስ ከፀጉሯ ላይ ያረፈች ሳር እያነሳ ‹‹ባታስተካክይውም ቆንጆ ነሽ ››አላት፡፡
ጉንጯ በእፍረት ቀላ‹‹ አመሰግናለው..ግን እንደምታየው ልብሴንም መቀየር አለብኝ?››
ራሄል አለባበሷ ለስራ ከምትለብሰው ልብስ ጋር ሲነፃፀር የተለመደ ነው ግን ሰሞኑን እቤት ስትውል ከምትለብሳቸው ልብሰች አንፃር በጣም ያጌጠና ያመረ የሚባል ነው፡፡
የዔሊያስ ተንኮል አዘል ፈገግታ ተፈታተናት፣ እጁ ዘንበል ብሎ አገጯን እየነካካ ‹‹ጸጉርሽን እንዲህ ስትለቂው ደስ ይለኛል.››ሲላት ለአፍታ ልብን የሚያቆም ፍርሀት ወረራት፡፡
‹‹እንደገና ሊስማኝ ነው እንዴ?›› ብላ በውስጧ አሰበች። እንዲያደርገው ፈለገች።
ፍርሀቷን በሳቅ ለመሸፈን እየጣረች ‹‹ፀጋ ሳትርቅ ብንሄድ ይሻለናል››አለችው፡፡
ወደፀጋ ሄዱና እያንዳንዳቸው አንዳንድ እጃን ያዙ. ራሄል ከሩቅ ለሚያያቸው ሰው ልክ ወደ ወ.ሮ ላምሮት ቤት ሲሄድ እንደነበሩት ቀን ቤተሰብ እንደሚመስሉ አሰበች። ።ወደጎን ዞር ብላ ስታየው ዓይናቸው ተገናኘ። ቢፌ በተደረደረበት ግዙፍ ጠረጴዛ አጠገብ ሲያልፉ የ ሰላጣ ሳህኖች ባዶ ሆነው አየችና እንደመበሳጨት ብላ‹‹ይቅርታ አድርግልኝ..ይህን ማስተካከል አለብኝ.››አለችውና ተለይታቸው ልትሄድ ስትል ዔሊያስ ፈጠን አለና እጇን በእጁ ያዘ።
‹‹አይ, ይሄ የአንቺ ስራ አይደለም, ሮቤል እና አዲሷ ረዳትሽ ሁሉንም ነገር በቁጥጥራቸው ስር አድርገውታል…ለእነሱ ተይላቸው.››አላት፡፡ራሄል ፊቷን አኮሰታተረች እና ተቃውሞዋን ልታሰማ ስትል አንዲት ተለቅ ያለች ነጭ ዩኒፎርም የለበሰች ሴት በላስቲክ የተሸፈነ ሳህን ይዛ መጣችና ባዶውን የሰላጣ ሳህን ስትሞለ ተመለከተች፡፡
ኤሊያስ ቅንድቡን ከፍ አድርጎ ‹‹አየሽ…ዘና በይ ..ሁሉ ነገር አሪፍ ይሆናል?››ሲል ተናገረ።ራሄል በራሷ ችኮነት አፍራ ሳቀች።
‹‹እሺ በቃ ዘና እላለሁ ።››አለችና ረዥሙ ትንፋሽ ሳበች ፣ ዙሪያውን ተመለከተች እና ይህንን እንደምትለምድ ተገነዘበች። የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቱ ብዙ ጊዜ የተጣደፈ ፣ የተቸኮለ ነበር፣አሁን የምታው ግን የተረጋጋ እና ዘና ያለ ሆኖ ነው ያገኘችው ፡፡አሁንም እየፈገገ ያለውን ዔሊን ተመለከተች እና ከሰዎች ጋር በቀላሉ መዋሀድ መቻል እንዴት ጥሩ እንደሆነ አሰበች። ዔሊም እያንዳንዱን እንግዳ ስታናግር ከጎኗ እንዲሆን ፈለገች።
ራሄል በሳቅ ፈገግታ ተጥለቅልቃ‹‹አስደናቂ ቀን ይሆናል ብዬ አስባለሁ››አለችው ።
ኤልያስም‹‹እንደዛ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ ።››ሲል ተጨማሪ ጥንካሬ ሰጣት።ከዚያም ራሄል ይቅርታ ጠየቀችውና አዲስ ወደገቡት እንግዶች ሄደች፡፡እሱ ፀጋን እንደያዘ በተወሰነ ርቀት ወደኃላ ቀረ፡፡ እንግዶቹን እያወራች ትኩረቷ በዔሊ ላይ ነበር።
ኤልያስ ዙሪያ ገባውን እየቃኘ የራሱን ትዝብት መውሰድ ጀመረ…አዎ እሱም እንደማንኛውም ሰው የራሱ እቅድ ነበረው፣ ነገር ግን ከዚህ ህዝብ ጋር ለመስማማት ትንሽ ከፍ ብሎ ማቀድ፣ ትንሽ መስራት፣ የአምስት አመት እቅድን ቢያንስ ወደ አስር አመት ማስፋፋት ይኖርበታል።እና የዛን ጊዜ በእንደዚህ አይነት ዝግጅት ላይ ከሚሳተፉ ከላይኛው ማህበረሰብ ሰዎች ጋር በደንብ ተቀላቅሎ ዘና ብሎ ማውራት ይችል ይሆናል..እስከዛው ግን እንደተነጠለ መቆየት መርጧል፡፡
በሀሳብ ተውጦ ሳለ ድንገት ከኋላው መጣችና‹‹ሰላም ነህ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ደህና ነኝ። ትንሽ የመጨናነቅ ስሜት እየተሰማኝ ነው።›› ሲል መለሰላት፡፡
‹‹ብዙ አዲስ ፊቶች ሲመጡ እያየው ነው›› አለች ራሄል ። ‹‹ግን ከጊዜ በኋላ ታውቋቸዋለህ። ››
‹‹ምናልባት››በማለት በአጭሩ መለሰላት፡፡
ራሄል የሆነ ነገር ልትናገር ስትል ሌላ ሰው ትኩረቷን ሳበው።የከተማዋ ከንቲባ ከባለቤታቸው ጋር ሲገቡ ተመለከተች፡፡ሞቅ ባለ ፈገግታ ኤሊያስን ወስዳ ከከንቲባውና ከባለቤቱ ጋር አስተዋወቀችው፡፡
‹‹ ክቡር ከንቲባ እናንተን በማየቴ ተደስቻለሁ››ስትል ራሄል ተናገረች ፡፡
‹‹እንደዚህ አይነት የተቀደሰ ስራ ላይ መገኘት ለእኛ ክብር ነው…ደግሞም አትርሺ ኃላፊነትም አለብን››ሲል ከንቲባው በኩራት መልስ ሰጡ
‹‹እና ይህቺ ትንሽ ልጅ የአንቺ ልጅ ነች?›› የከንቲባው ባለቤት በዔሊያስ እና ራሄል እጆች ላይ ወደተንጠለጠለችው ወደ ፀጋ እያመለከተች ጠየቀች።
ራሄል ሳቀች። ‹‹አይ ይህች እህቴ ነች። ወላጆቻችን ከህጻናት ማሳደጊያ ተቋሞች በማደጎ ወሰደዋት ነው። እናቴ ከወደቀችበት አስክታገግም እኔ እየተንከባከብኳት ነው። ዶ/ር ዔሊያስ የህፃናት ሐኪም ነው..የእሷን ጤና የሚከታተለው እሱ ነው።››ሰትል ማብራሪያ ሰጠች፡፡
‹የእሷ ሐኪም ነው …. ?ምን ያህል አስደሳች ነው.››አለች የከንቲባው ሚስት፡፡
ጋጠወጥ በሚመስለው ንግግሯ ብስጭት ያለው ኤልያስ ፍርጥም ብሎ ‹‹በእርግጥ አዎ..የእሷ ሀኪም ነኝ…ልጆችን ማከምና መንከባከብ በጣም ፈታኝ ከሆኑ የሕክምና ክፍሎች ውስጥ አንዱና ዋነኛው ነው . ነገር ግን ከህፃናት በጣም የምወደው ነገር ሙሉ በሙሉ ሐቀኛ መሆናቸው ነው››ሲል መለሰላት፡፡
የሴትዬዋ አይኖች ጠበቡ፣ እና ዔሊ የተሳሳተ ነገር ተናግሮ ሊሆን እንደሚችል ተረዳ። ቢሆንም ብዙም አልተፀፀትም… ሴትዬዋ የከንቲባው ሚስት ልትሆን ትችላለች፣ ነገር ግን ይህ ለእሱ ምንም ትርጉም አልነበረውም።
ከንቲባው ወደ ፀጋ ተመለከተ። ‹‹ስለዚህ ይህቺ ቆንጅዬ ልጅ ከማደጎ ቤት የተገኘች ነች እያልሺኝ ነው፡፡ይህ ልጅ እንዲኖራቸው ለሚመኙ ወላጆችዎ አንድ እርምጃ ነው.፡፡ ›› ከዛ ትንፋሽ ወሰደና ንግግሩን ቀጠለ‹‹እኔና ባለቤቴ ልጅ መውለድ አልተሳካልንም…በጉዲፈቻ ወስደን ለማሳደግ አስበን ነበር …ነገር ግን እርግጠኛ መሆን አልቻልንም ። በጉዲፈቻ ለማሳደግ ስንወስን ምን አይነት ልጅ እንደሚያጋጥመን አናውቅም እና ስለ ወላጆቻቸውም በቂ እውቀት ማግኘት ቀላል ስራ አይደለም፤ብቻ ውስብስብ ሆኖ ነው ያገኘነው።››
ዔሊያስ በከንቲባው ቅጥ አንባሩ የጠፋ ቀፋፊ ንግግር ሽምቅቅ አለ… ንዴቱን ለመቆጣጠር እየጣረ ነው፡፡ ሁኔታውን የተረዳቸው ራሔል በጨረፍታ ተመለከተችው፣ እሷ ግን በሴትዬዋ መውለድ አለመቻል ልቧ ተነክቶ በአዘኔታ እየተመለከተች ነበር።ስለዚህ ጣልቃ ገባች፡፡ ‹‹ጉዲፈቻ ለሁሉም ሰው የሚሆን አይደለም››ስትል በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ተናግረች።
ሴትዬዋ ወደከንቲባው ጆሮ ተጠግታ የማይሰማ ነገር አንሾካሾከችለት።ከዛ ወደራሄል ዞር አለና ‹‹ይቅርታ ካደረግሽልኝ እባክሽ ሚስቴ ጥሩ ስሜት እየተሰማት አይደለም..መሄድ አለብን››ሲል የራሄልን ፍቃድ ጠየቀ፡፡
‹‹በጣም ይቅርታ.. ስለመጣችሁ አመሰግናለው….መሄድ ትችላላችሁ… ወይ ከፈለግክ ወደ ቤት አስገባት።››ባለቤቱ ጭንቅላቷን ባለመስማማት ነቀነቀች።
‹‹አመሰግናለሁ፣ ግን ወደቤት መሄድ ይሻለኛል።››
ባልና ሚስቶቹ ተያይዘው ወደመኪናቸው ሄዱ….አጃቢዎቻቸው ከበው ተከተሏቸው።
‹‹ለሚዲያ ፊታቸውን ለማሳየትና ለዜና የሚሆን ፎቶ ለመነሳት ነበር የመጡት…ሲጨርሱ ሄዱ››አላት ኤልያስ፡፡
‹‹አዎ ግን ትርፉ የጋራ ነው…ከዚህ አይነት አስመሳይ ድርጊታቸው እኛም በጣም ተጠቃሚ ነው የምንሆነው..ምንም ቢሆን ፓለቲካዊ ኃይሉ እንሱ እጅ መሆኑን እንዳትዘነጋ››አለችው
‹‹ምን ፖሊቲካዊ ብቻ ኢኮኖሚያዊ ኃይሉም ተጠቅልሎ እነሱ ስር ነው ያለው››
በመሃከላቸው ወ.ሮ ላምሮት ስትመጣ ነበር ..ውይይታቸውን ያቆሙት፡፡
‹‹ጤና ይስጥልኝ ወ.ሮ ላምሮት››አለች ራሄል ፈገግ ብላ ፡፡
‹‹እናንተስ እንዴት ናችሁ.?››.ፀጋን ጨምሮ ሶስቱንም በየተራ ሳመቻቸው፡፡
‹‹በመምጣትሽ በጣም ደስ ብሎኛል ››
ወይዘሮዋ በፈገግታዋ እንደደመቀች ወደቦርሳዋ ገባችና የሆነ ወረቀት አውጥታ ወደራሄል ዘረጋች…ራሄል ግራ በመጋባት ተቀበለቻት…ቼክ ነበር…ከፋታ ስታዬው መጀመሪያ አገኛለው ብላ እሷ ጋር ስትመላለስ ከነበረው ብር ብዙ ብልጫ ያለው ነበር፡፡
‹‹ሁሉ ነገርሽ ስላስደሰተኝ…ይሄንን ሳረግ በፍፅም መተማመን እና በደስታ ነው››የሚል ቃል አከለችበት፡፡
ራሄል ምንም ቃል ከመናገሯ በፊት ተንደረደረችና መልሳ አቀፈቻት፡፡
ለትንሽ ጊዜ ተጨዋወቱ፣ ከዚያም ራሄል በሌላ ሰው ተጠርታ ሄደች፡፡ወ.ሮ ላምሮትም ኤልያስን ተሰናብታ ከመሰል ከጓደኞቾ ጋር ተቀላቀለች፡፡
ከኤልያስ ጋር የቀረችው ፀጋም የራሄል ጓደኛ የሆነችውን የሌንሳን መንታ ልጆችን ስታገኝ እሱን ጥላ ከእነሱ ጋር ለመጫወት ሄደች፡፡
ዔሊያስ ብቻውን ሲሆን በነፃነት ግቢውን መጎብኘት ጀመረ ፡፡ባለፈው አባቷ ዙሪያውን በሚያሳዩት ወቅት ጉብኝቱ በመዋኛ ገንዳው ዙሪያ ባሉ የአትክልት ስፍራዎች ብቻ የተገደበ ነበር ።ጊቢው እንዲህ በጣም ሰፊ እንደሆነ አያውቅም ነበር። አንድ ቀን ይህ ሁሉ የራሔል ንብረት መሆኑ አይቀርም ሲል አሰበ። እንደዛ በማሰብ እራሱን ታዘበ፡፡
በአጠቃላይ የእለቱ ፕሮግራም ራሄል ካሰበችው በላይ እጅግ ውጤታማ ከታቀደው በላይ ገቢ የተገኘበትና እሷም የረካችበት ሆኖ ተጠናቀቀ፡፡
መጀመሪያውኑ በዝግጅቱ ላይ እንዲገኝ ስትጋብዘው ራሔል በሥራ እንደምትጠመድ ያውቅ ነበር፣ በተለይ ዝግጅቱ ወደማለቂያው ሲቃረብ ሁሉም ለመጨረሻ ጊዜ ከእሷ ጋር ተገናኝቶ ማውራት ይፈልግ ስለነበረ ከእሱ ጋር ለመሆን ምንም አይነት ሽራፊ ደቂቀ ማግኘት አልቻለችም…ለዛ ነው ብቻውን ለረጅም ጊዜ ጊቢ ውስጥ እየዞረ እያንዳንዱን የግቢውን ስፍራ አብጠርጥሮ ሲጎበኝ የነበረው….ከዛ የፀጋን የለቅሶ ድምፅ ሰማና ወደ ሳሎን ሲገባ ከራሄል ጓደኛ መንታ ልጆች ጋር ተጣልታ አገኛት…ከዛ በኃላ ነው አባብሎ ወደውስጠኛው ክፍል ይዞት የገባው፡፡
በእቅፉ ውስጥ ሆና እየተጠማዘዘችና እና እያንገላታች አስቸገረችው። ሰውነቷ በመጠኑ ሞቃት ነበር ፡፡ ወደ ክፍሏ ወስዶ ሊያስተኛት ሞከረ፣ እሷ ግን ከእሱ ጋር ተጣበቀች‹‹መተኛት ትፈልጊያለሽ?››ጠየቃት….ጮክ ብላ ጭንቅላቷን በአሉታ ነቀነቀች፣ ፡፡
‹‹አልጋ አልፈልግም …አልጋ አልፈልግ››ስትል ቀወጠችው፡፡
‹‹እሺ ሰማሁሽ።››ከእርሷ ጋር የሚቀመጥበትን ቦታ ለማግኘት እየሞከረ ትልቁና ሰፊው ደረጃ ተጠቅሞ ወደ ኮሪደሩ ወረደ። ዴስክ እና አንዳንድ ወንበሮችን የያዘ ትልቅ ክፍል አገኘና አልፎ ወደ ውስጥ ገባ።ራሄል እንደ ቢሮዋ የምትጠቀምበት ክፍል ሊሆን እንደሚችል ገመተ። ወረቀቶች በጠረጴዛው ተዘርግተው ነበር ፣ ለእሱ ምቹ መስሎ የታየውን ግዙፍ የሆነውን የቆዳ ወንበር ላይ በእፎይታ ቁጭ አለ፡፡ዝግጅቱ ለእሱ ብዙም ሚያስደስት አይነት ባይሆንም ለራሄል ወሳኝ እና አስፈላጊ እንደሆነ ስለሚያስብ ሁሉን ነገር በትእግስት አሳልፉ ነው ወደመጨረሻው የደረሰው…አሁን ግን እሱም እንደፀጋ ዝሏል።
ከዛም አልፎ እንቅልፍ ሊጥለው እየተፈታተነው ነው።ፀጋን እንዳቀፈ ጭንቅላቱን የግዙፉ ወንበር መደገፊያ ላይ ደገፍ አደረገ
ራሄል የሆነ ነገር ልትናገር ስትል ሌላ ሰው ትኩረቷን ሳበው።የከተማዋ ከንቲባ ከባለቤታቸው ጋር ሲገቡ ተመለከተች፡፡ሞቅ ባለ ፈገግታ ኤሊያስን ወስዳ ከከንቲባውና ከባለቤቱ ጋር አስተዋወቀችው፡፡
‹‹ ክቡር ከንቲባ እናንተን በማየቴ ተደስቻለሁ››ስትል ራሄል ተናገረች ፡፡
‹‹እንደዚህ አይነት የተቀደሰ ስራ ላይ መገኘት ለእኛ ክብር ነው…ደግሞም አትርሺ ኃላፊነትም አለብን››ሲል ከንቲባው በኩራት መልስ ሰጡ
‹‹እና ይህቺ ትንሽ ልጅ የአንቺ ልጅ ነች?›› የከንቲባው ባለቤት በዔሊያስ እና ራሄል እጆች ላይ ወደተንጠለጠለችው ወደ ፀጋ እያመለከተች ጠየቀች።
ራሄል ሳቀች። ‹‹አይ ይህች እህቴ ነች። ወላጆቻችን ከህጻናት ማሳደጊያ ተቋሞች በማደጎ ወሰደዋት ነው። እናቴ ከወደቀችበት አስክታገግም እኔ እየተንከባከብኳት ነው። ዶ/ር ዔሊያስ የህፃናት ሐኪም ነው..የእሷን ጤና የሚከታተለው እሱ ነው።››ሰትል ማብራሪያ ሰጠች፡፡
‹የእሷ ሐኪም ነው …. ?ምን ያህል አስደሳች ነው.››አለች የከንቲባው ሚስት፡፡
ጋጠወጥ በሚመስለው ንግግሯ ብስጭት ያለው ኤልያስ ፍርጥም ብሎ ‹‹በእርግጥ አዎ..የእሷ ሀኪም ነኝ…ልጆችን ማከምና መንከባከብ በጣም ፈታኝ ከሆኑ የሕክምና ክፍሎች ውስጥ አንዱና ዋነኛው ነው . ነገር ግን ከህፃናት በጣም የምወደው ነገር ሙሉ በሙሉ ሐቀኛ መሆናቸው ነው››ሲል መለሰላት፡፡
የሴትዬዋ አይኖች ጠበቡ፣ እና ዔሊ የተሳሳተ ነገር ተናግሮ ሊሆን እንደሚችል ተረዳ። ቢሆንም ብዙም አልተፀፀትም… ሴትዬዋ የከንቲባው ሚስት ልትሆን ትችላለች፣ ነገር ግን ይህ ለእሱ ምንም ትርጉም አልነበረውም።
ከንቲባው ወደ ፀጋ ተመለከተ። ‹‹ስለዚህ ይህቺ ቆንጅዬ ልጅ ከማደጎ ቤት የተገኘች ነች እያልሺኝ ነው፡፡ይህ ልጅ እንዲኖራቸው ለሚመኙ ወላጆችዎ አንድ እርምጃ ነው.፡፡ ›› ከዛ ትንፋሽ ወሰደና ንግግሩን ቀጠለ‹‹እኔና ባለቤቴ ልጅ መውለድ አልተሳካልንም…በጉዲፈቻ ወስደን ለማሳደግ አስበን ነበር …ነገር ግን እርግጠኛ መሆን አልቻልንም ። በጉዲፈቻ ለማሳደግ ስንወስን ምን አይነት ልጅ እንደሚያጋጥመን አናውቅም እና ስለ ወላጆቻቸውም በቂ እውቀት ማግኘት ቀላል ስራ አይደለም፤ብቻ ውስብስብ ሆኖ ነው ያገኘነው።››
ዔሊያስ በከንቲባው ቅጥ አንባሩ የጠፋ ቀፋፊ ንግግር ሽምቅቅ አለ… ንዴቱን ለመቆጣጠር እየጣረ ነው፡፡ ሁኔታውን የተረዳቸው ራሔል በጨረፍታ ተመለከተችው፣ እሷ ግን በሴትዬዋ መውለድ አለመቻል ልቧ ተነክቶ በአዘኔታ እየተመለከተች ነበር።ስለዚህ ጣልቃ ገባች፡፡ ‹‹ጉዲፈቻ ለሁሉም ሰው የሚሆን አይደለም››ስትል በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ተናግረች።
ሴትዬዋ ወደከንቲባው ጆሮ ተጠግታ የማይሰማ ነገር አንሾካሾከችለት።ከዛ ወደራሄል ዞር አለና ‹‹ይቅርታ ካደረግሽልኝ እባክሽ ሚስቴ ጥሩ ስሜት እየተሰማት አይደለም..መሄድ አለብን››ሲል የራሄልን ፍቃድ ጠየቀ፡፡
‹‹በጣም ይቅርታ.. ስለመጣችሁ አመሰግናለው….መሄድ ትችላላችሁ… ወይ ከፈለግክ ወደ ቤት አስገባት።››ባለቤቱ ጭንቅላቷን ባለመስማማት ነቀነቀች።
‹‹አመሰግናለሁ፣ ግን ወደቤት መሄድ ይሻለኛል።››
ባልና ሚስቶቹ ተያይዘው ወደመኪናቸው ሄዱ….አጃቢዎቻቸው ከበው ተከተሏቸው።
‹‹ለሚዲያ ፊታቸውን ለማሳየትና ለዜና የሚሆን ፎቶ ለመነሳት ነበር የመጡት…ሲጨርሱ ሄዱ››አላት ኤልያስ፡፡
‹‹አዎ ግን ትርፉ የጋራ ነው…ከዚህ አይነት አስመሳይ ድርጊታቸው እኛም በጣም ተጠቃሚ ነው የምንሆነው..ምንም ቢሆን ፓለቲካዊ ኃይሉ እንሱ እጅ መሆኑን እንዳትዘነጋ››አለችው
‹‹ምን ፖሊቲካዊ ብቻ ኢኮኖሚያዊ ኃይሉም ተጠቅልሎ እነሱ ስር ነው ያለው››
በመሃከላቸው ወ.ሮ ላምሮት ስትመጣ ነበር ..ውይይታቸውን ያቆሙት፡፡
‹‹ጤና ይስጥልኝ ወ.ሮ ላምሮት››አለች ራሄል ፈገግ ብላ ፡፡
‹‹እናንተስ እንዴት ናችሁ.?››.ፀጋን ጨምሮ ሶስቱንም በየተራ ሳመቻቸው፡፡
‹‹በመምጣትሽ በጣም ደስ ብሎኛል ››
ወይዘሮዋ በፈገግታዋ እንደደመቀች ወደቦርሳዋ ገባችና የሆነ ወረቀት አውጥታ ወደራሄል ዘረጋች…ራሄል ግራ በመጋባት ተቀበለቻት…ቼክ ነበር…ከፋታ ስታዬው መጀመሪያ አገኛለው ብላ እሷ ጋር ስትመላለስ ከነበረው ብር ብዙ ብልጫ ያለው ነበር፡፡
‹‹ሁሉ ነገርሽ ስላስደሰተኝ…ይሄንን ሳረግ በፍፅም መተማመን እና በደስታ ነው››የሚል ቃል አከለችበት፡፡
ራሄል ምንም ቃል ከመናገሯ በፊት ተንደረደረችና መልሳ አቀፈቻት፡፡
ለትንሽ ጊዜ ተጨዋወቱ፣ ከዚያም ራሄል በሌላ ሰው ተጠርታ ሄደች፡፡ወ.ሮ ላምሮትም ኤልያስን ተሰናብታ ከመሰል ከጓደኞቾ ጋር ተቀላቀለች፡፡
ከኤልያስ ጋር የቀረችው ፀጋም የራሄል ጓደኛ የሆነችውን የሌንሳን መንታ ልጆችን ስታገኝ እሱን ጥላ ከእነሱ ጋር ለመጫወት ሄደች፡፡
ዔሊያስ ብቻውን ሲሆን በነፃነት ግቢውን መጎብኘት ጀመረ ፡፡ባለፈው አባቷ ዙሪያውን በሚያሳዩት ወቅት ጉብኝቱ በመዋኛ ገንዳው ዙሪያ ባሉ የአትክልት ስፍራዎች ብቻ የተገደበ ነበር ።ጊቢው እንዲህ በጣም ሰፊ እንደሆነ አያውቅም ነበር። አንድ ቀን ይህ ሁሉ የራሔል ንብረት መሆኑ አይቀርም ሲል አሰበ። እንደዛ በማሰብ እራሱን ታዘበ፡፡
በአጠቃላይ የእለቱ ፕሮግራም ራሄል ካሰበችው በላይ እጅግ ውጤታማ ከታቀደው በላይ ገቢ የተገኘበትና እሷም የረካችበት ሆኖ ተጠናቀቀ፡፡
መጀመሪያውኑ በዝግጅቱ ላይ እንዲገኝ ስትጋብዘው ራሔል በሥራ እንደምትጠመድ ያውቅ ነበር፣ በተለይ ዝግጅቱ ወደማለቂያው ሲቃረብ ሁሉም ለመጨረሻ ጊዜ ከእሷ ጋር ተገናኝቶ ማውራት ይፈልግ ስለነበረ ከእሱ ጋር ለመሆን ምንም አይነት ሽራፊ ደቂቀ ማግኘት አልቻለችም…ለዛ ነው ብቻውን ለረጅም ጊዜ ጊቢ ውስጥ እየዞረ እያንዳንዱን የግቢውን ስፍራ አብጠርጥሮ ሲጎበኝ የነበረው….ከዛ የፀጋን የለቅሶ ድምፅ ሰማና ወደ ሳሎን ሲገባ ከራሄል ጓደኛ መንታ ልጆች ጋር ተጣልታ አገኛት…ከዛ በኃላ ነው አባብሎ ወደውስጠኛው ክፍል ይዞት የገባው፡፡
በእቅፉ ውስጥ ሆና እየተጠማዘዘችና እና እያንገላታች አስቸገረችው። ሰውነቷ በመጠኑ ሞቃት ነበር ፡፡ ወደ ክፍሏ ወስዶ ሊያስተኛት ሞከረ፣ እሷ ግን ከእሱ ጋር ተጣበቀች‹‹መተኛት ትፈልጊያለሽ?››ጠየቃት….ጮክ ብላ ጭንቅላቷን በአሉታ ነቀነቀች፣ ፡፡
‹‹አልጋ አልፈልግም …አልጋ አልፈልግ››ስትል ቀወጠችው፡፡
‹‹እሺ ሰማሁሽ።››ከእርሷ ጋር የሚቀመጥበትን ቦታ ለማግኘት እየሞከረ ትልቁና ሰፊው ደረጃ ተጠቅሞ ወደ ኮሪደሩ ወረደ። ዴስክ እና አንዳንድ ወንበሮችን የያዘ ትልቅ ክፍል አገኘና አልፎ ወደ ውስጥ ገባ።ራሄል እንደ ቢሮዋ የምትጠቀምበት ክፍል ሊሆን እንደሚችል ገመተ። ወረቀቶች በጠረጴዛው ተዘርግተው ነበር ፣ ለእሱ ምቹ መስሎ የታየውን ግዙፍ የሆነውን የቆዳ ወንበር ላይ በእፎይታ ቁጭ አለ፡፡ዝግጅቱ ለእሱ ብዙም ሚያስደስት አይነት ባይሆንም ለራሄል ወሳኝ እና አስፈላጊ እንደሆነ ስለሚያስብ ሁሉን ነገር በትእግስት አሳልፉ ነው ወደመጨረሻው የደረሰው…አሁን ግን እሱም እንደፀጋ ዝሏል።
ከዛም አልፎ እንቅልፍ ሊጥለው እየተፈታተነው ነው።ፀጋን እንዳቀፈ ጭንቅላቱን የግዙፉ ወንበር መደገፊያ ላይ ደገፍ አደረገ
ራሄል ዔሊያስን እና ፀጋን ፍለጋ ወደ ቤት ገባች። ወጥ ቤቱ እና ኮሪደሩ ከቤት ውጭ ካለው ሙቀት ጋር ሲነፃፀሩ ጥሩ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት። በተለምዶ እሷ ሰራተኞቿን ታዛለች፣ ከሰዎች ጋር ታወራለች፣ ምግብ ሰጪዎችን፣ የምግብ አቅርቦቱን እየተከታተለች፣ ማንም ሰው ችላ እንዳልተባለ ታረጋግጣለች እንጂ ከዝግጅቶቾ መካከል ሾልካ ለመውጣት አትደፍርም ነበር። ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ፣ ለሮቤል እና ለአዲሷ ረዳት ምስጋና ይግባቸውና እንደቀደሙት ዓመታት እስክትዝል ድረስ መድከም አላስፈለጋትም ። እና፣ ከስብሰባ እና ከእንግዶች አጀብ መካከል ሾልካ ወጥታ ዔሊያስ ከፀጋ ጋር የት እንዳሉ ለማወቅ ጊዜ አግኝታለች ፡፡ እነሱ ፎቅ ላይ፣ ወይም ሳሎን ውስጥ፣ ወይም በቤተሰብ ክፍል ውስጥ አልነበሩም። ከአባቷ ጥናት ክፍል የሆነ ድምፅ የሰማች መሰላት። ፀጋ ስትተኛ የምታሰማው አይነት ድምፅ ነበር።በሩን ወደ ፊት ገፋ ስታደርግ የዔሊያስ ጭንቅላት የወንበሩ መደገፊያ ላይ ተደግፎ አየች። ወደ ክፍሉ ስትገባ፣ በአባቷ ተወዳጅ ወንበር ላይ ተቀምጦ እንቅልፍ የወሰደው ረጅም ሰው በማየቷ ከፍተኛ መገረም ውስጥ ገባች ፡፡ ፀጋ በእቅፉ ውስጥ ሆና ተጠምጥማበታለች።ዔሊ በሚገርም ሁኔታ ዘና ብሎ በእንቅልፍ ውስጥ ነው ፣ እሷ በተቃራኒው ወንበር ላይ ተቀመጠች፣ ለአሁን በፀጥታ በማየት ብቻ ሁኔታውን በጥልቀት መታዘብ ነው የፈለገችው፡፡ከዛ በድንገት ፀጋ በእንቅልፍ ልቧ ጮኸች ወዲያው የዔሊያስ አይኖች ተገለጡ። ግራ የተጋባ መስሎ ዙሪያውን ተመለከተ፣ ለጥቂት ጊዜ አይኖቹን ከፈት ዘጋ አደረገ ። ከዚያም ራሄልን አይቶ ዘና አለ።
በጸጥታ ፀጋን አስተካክሎ አቀፋትና‹‹ ይቅርታ›› አለ ።ራሄል ተነሳች እና በለሆሳስ ፀጋን ከእቅፉ በመውሰድ ‹‹ወደ መኝታዋ እወስዳታለው››አለችው፡፡በስሱ ፈገግታ ሰጣት።
ከእንቅልፍ ስሜት ሙሉ በሙሉ እንዳልተላቀቀ በሚያሳብቅ ቅላፄ‹‹እኔ እዚህ እቆያለሁ›› አለ፣ ።ራሄል ስለኤሊያስና እሷ በስሜት መሳሳብ እያሰበች ደረጃውን በዝግታ ወጣች። ነገሮች በፍጥነት እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ተሰምቷታል ።ፀጋን አልጋዋ ላይ በማስተኛት በአግባቡ ሸፍነቻት። መብራቱን ለማረጋገጥ የሕፃኑን መቆጣጠሪያ ተመለከተች። ባለችበት ቆይታ እየሆኑ ስላሉ ነገሮች ለማሰብ ፈልጋ ነበር።ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ለማወቅ ሞክረች. ነገር ግን የተፈጥሮ ጥንቃቄዋን መሻር ከዔሊያስ ጋር የመሆን ፍላጎት ወሰወሳት። ወደ እሱ ስትመለስ ሙሉ በሙሉ ነቅቶ ወደ ቆዳ ሶፋ ተዛውሮ ነበር። በሌላኛው ወንበር ላይ መቀመጥ ትችል ነበር . ነገር ግን ወደኃላ ሚገፋትን ስሜት ተቋቁማ እሱ በተቀመጠበት ሶፋ ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹እሺ ተረጋጋች?›› ዔሊ ጠየቀ፣ ድምፁ ረጋ ያለ ነው።
‹‹አዎ…ተኝታለች."
ልክ የሆነ ደስ የሚል ቦታ ሆና ጉብኝት ላይ ያለች መስሎ እየተሰማት ነው ፡፡ ወደ ግቢው ሲመጣ ካየችው ጀምሮ ያሰበችው ነገር አለ።‹‹እዚህ ለተወሰነ ጊዜ መቆየት እችላለሁ››ምንም አላላትም፣ አይኖቹ እሷ ላይ ናቸው። ከዚያም ወደ እሷ ቀረበና ፊቷን በእጁ ሸፍኖ ከሰአት በኋላ ያየችውን ቃል በዓይኑ አቀረበ። እጆቾን ጠምዝዞ ወደራሱ አስጠጋት እና ሳማት።ራሄል እጆቿን በአንገቱ ላይ ጠመጠመችና ጣቶቿን በፀጉሩ ላይ በማድረግ ታሻሸው ጀመር… ልቧ ወደ ጉሮሮዋ የመጣ መሰላት።
‹‹ዛሬ ካየሁህ ከመጀመሪያው ጊዜ ጀምሮ እንዲህ ላደርግ ፈልጌ ነበር››ብላ ተናዘዘችለት፡፡ጸጉሯን ከፊቷ ላይ እየገለጠ በትኩረት እሷን ከማየት ውጭ ምንም ማለት አልቻለችም። ይህች ቅጽበት በጊዜ የታገደች ያህል ተሰማት፣ ከቀሪው ሕይወቷ የተለየ የስሜት ፏፏቴ የሚንዠቀዘቅባት እንደሆነች አመነች። ከአንድ ወንድ ጋር ከተጣመረች በጣም ረጅም ጊዜ አልፏታል።
‹‹እዚህ ምን እየሆነ ነው ራሄል?›› ዔሊያስ በመጨረሻ ጠየቃት፣
ጥያቄውን ላለፉት ሳምንታት ለመፍታት ስትሞክር የነበረውን ስሜትን ወደ ሀሳቧ አመጣ።
‹‹አላውቅም።›› አለችና በመጠኑ ከእሱ አፈገፈገች ፡፡ በዚህ ቅጽበት ከእሱ ጋር ለመደሰት ፈልጋለች። የበለጠ ልታውቀው ፈልጋለች። ከራሷም የሸሸገችውን ነገር አስቀድሞ ከእርሱ ጋር ተጋርታለች።ዝግ ሆኖ ለአመታት የቆየውን የሕይወቷ ክፍል ውስጥ ቀስ በቀስ ቢሆንም እያስገባችው ነው።እንደገና እንዲስማት ፈቅዳለት ነበር። እና እንደገና ልትስመው ፈለገች።እና ወደ እሷ ሲጠጋ፣ ልቧ ተናወጠ እና በጉጉት ቀዘቀዘ።
‹‹ደግመህ ልታደርገው ነው?.››አይኖቹ መንገዳቸውን እየተከተሉ ነው።
‹‹ ደጋግሜ ከማድረግ ውጭ ምርጫ የለኝም….የሚጠገብ አይነት ነገር አይደለም...››አላት
‹‹እሺ እንደፈለክ››አለችና ደረቱ ላይ ተለጠፈችበት፡፡
‹‹ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ እንደማያውቅ አውቃለሁ። ይህ ሊሆን ይችላል ብዬ አላሰብኩም ነበር።››የተስፋውን ቃል በቃሉ ሰማች።
ቀጠለ‹‹መጀመሪያ ስታገኚኝ የወደድሺኝ አይመስለኝም ነበር›› አላት
‹‹በሞተር ሳይክል ስለነበርክ ነው››
ጣቶቹን በፀጉሯ ውስጥ ተርመሰመሰ፣ ማዕበላቸውን አስተካክሎ፣ ብርሃን በመላ ሰውነታቸው እየተንቦገቦገ ነው ።በሌላ ሰው እጅ ቁጥጥር ስር በገመድ ላይ እንዳለ ካይት በቀስታ ወደ ላይ የምትንሳፈፍ አይነት ስሜት ተሰማት። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ፣ በህይወቷ ውስጥ ሌላ ሰው የማግኘት ተስፋው አስደሰታት።አሁን ያለፈ ህይወቷን ለመልቀቅ ዝግጁ ነበረች? በህይወቷ ውስጥ እሱን ሙሉ በሙሉ ለማሳተፍ ፍቃደኛ ሆናለች፡፡ሀሳቡ የጋለ ስሜት እና የፍርሃት ውህደት እንዲሰማት አደረጋት።አሁን በድጋሚ ብትስመው ምን ይሆናል?
‹‹ራሄል፣ እዚህ ነሽ?››የለሊሴን ድምፅ ከኩሽና ተጣራ፣ ራሄልን ወደ እውነታው ተመንጭቃ ተመለሰች።
ከተቀመጠችበት ተነሳችና ቆመች…ጎተተና እንደገና ሳማት።የወሰደው እርምጃ የራሄልን ልብ አቀለጠው። ራሷን በጣም ርቃ እንድትንሳፈፍ የፈቀደች ያህል ተሰማት። ስሜቶች ህይወቷን እንዲቆጣጠሩ ያደረጋትን ጠንካራ መሰረት ተቀብለዋለች።
‹‹አሁን መሄድ አለብኝ››
‹‹እሺ ሂጂ››
ራሄል ሁል ጊዜ ሰዎች በሚፈልጉበት መንገድ እንደማይሄዱ ታውቃለች። ኪሩቤል በአደጋ ሆስፒታል ገብቶ በህመም እየተሰቃየ ለሞት ሲያጣጥር ረጅም እና ጠንክራ ፀሎት ስትጸልይ ነበር። አሁንም ግን በእግዚአብሔር ለመታመን ዝግጁ መሆኗን እርግጠኛ አልነበረችም።
‹‹ደስተኛ መሆን የሚገባኝ ይመስለኛል››ስትል ለራሷ አጉተመተመች፡፡
በዚህ ግንኙነታቸው ውስጥ እሷ እየመራችው እንደሆነ ተሰምቷታል, ግን በተመሳሳይ ጊዜ ስለ ስሜቷ እርግጠኛ አልነበረችም. ምን ማድረግ እንዳለባትም እርግጠኛ አይደለችም. እንደገና ራሷን ለጥቃት የተጋለጠች ለማድረግ እንደደፈረች አላወቀችም።እሱ ጥሩ ….ደግ እና ጨዋ ነበር። እና ባየችው ቁጥር ለእሱ ያላት ስሜት እየጠነከረ ነው የሄደው። በህይወቷ ውስጥ የት እንደምታስቀምጠው ለማወቅ ትንሽ ጊዜ ያስፈልጋታል።
‹‹ታውቃለህ አይደል..እንደዚህ ማድረግ አልነበረብንም››አለችው….አንደበቷ ከልቧ ተቃራኒ የሆኑ ቃላቶቸን ነው ያወጣው፡፡ ሃሳቧን ቀይራ መልሳ ደረቱ ላይ ከመለጠፏ በፊት ‹‹እዚህ ነኝ ለሊሴ››እያለች ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
በጸጥታ ፀጋን አስተካክሎ አቀፋትና‹‹ ይቅርታ›› አለ ።ራሄል ተነሳች እና በለሆሳስ ፀጋን ከእቅፉ በመውሰድ ‹‹ወደ መኝታዋ እወስዳታለው››አለችው፡፡በስሱ ፈገግታ ሰጣት።
ከእንቅልፍ ስሜት ሙሉ በሙሉ እንዳልተላቀቀ በሚያሳብቅ ቅላፄ‹‹እኔ እዚህ እቆያለሁ›› አለ፣ ።ራሄል ስለኤሊያስና እሷ በስሜት መሳሳብ እያሰበች ደረጃውን በዝግታ ወጣች። ነገሮች በፍጥነት እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ተሰምቷታል ።ፀጋን አልጋዋ ላይ በማስተኛት በአግባቡ ሸፍነቻት። መብራቱን ለማረጋገጥ የሕፃኑን መቆጣጠሪያ ተመለከተች። ባለችበት ቆይታ እየሆኑ ስላሉ ነገሮች ለማሰብ ፈልጋ ነበር።ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ለማወቅ ሞክረች. ነገር ግን የተፈጥሮ ጥንቃቄዋን መሻር ከዔሊያስ ጋር የመሆን ፍላጎት ወሰወሳት። ወደ እሱ ስትመለስ ሙሉ በሙሉ ነቅቶ ወደ ቆዳ ሶፋ ተዛውሮ ነበር። በሌላኛው ወንበር ላይ መቀመጥ ትችል ነበር . ነገር ግን ወደኃላ ሚገፋትን ስሜት ተቋቁማ እሱ በተቀመጠበት ሶፋ ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹እሺ ተረጋጋች?›› ዔሊ ጠየቀ፣ ድምፁ ረጋ ያለ ነው።
‹‹አዎ…ተኝታለች."
ልክ የሆነ ደስ የሚል ቦታ ሆና ጉብኝት ላይ ያለች መስሎ እየተሰማት ነው ፡፡ ወደ ግቢው ሲመጣ ካየችው ጀምሮ ያሰበችው ነገር አለ።‹‹እዚህ ለተወሰነ ጊዜ መቆየት እችላለሁ››ምንም አላላትም፣ አይኖቹ እሷ ላይ ናቸው። ከዚያም ወደ እሷ ቀረበና ፊቷን በእጁ ሸፍኖ ከሰአት በኋላ ያየችውን ቃል በዓይኑ አቀረበ። እጆቾን ጠምዝዞ ወደራሱ አስጠጋት እና ሳማት።ራሄል እጆቿን በአንገቱ ላይ ጠመጠመችና ጣቶቿን በፀጉሩ ላይ በማድረግ ታሻሸው ጀመር… ልቧ ወደ ጉሮሮዋ የመጣ መሰላት።
‹‹ዛሬ ካየሁህ ከመጀመሪያው ጊዜ ጀምሮ እንዲህ ላደርግ ፈልጌ ነበር››ብላ ተናዘዘችለት፡፡ጸጉሯን ከፊቷ ላይ እየገለጠ በትኩረት እሷን ከማየት ውጭ ምንም ማለት አልቻለችም። ይህች ቅጽበት በጊዜ የታገደች ያህል ተሰማት፣ ከቀሪው ሕይወቷ የተለየ የስሜት ፏፏቴ የሚንዠቀዘቅባት እንደሆነች አመነች። ከአንድ ወንድ ጋር ከተጣመረች በጣም ረጅም ጊዜ አልፏታል።
‹‹እዚህ ምን እየሆነ ነው ራሄል?›› ዔሊያስ በመጨረሻ ጠየቃት፣
ጥያቄውን ላለፉት ሳምንታት ለመፍታት ስትሞክር የነበረውን ስሜትን ወደ ሀሳቧ አመጣ።
‹‹አላውቅም።›› አለችና በመጠኑ ከእሱ አፈገፈገች ፡፡ በዚህ ቅጽበት ከእሱ ጋር ለመደሰት ፈልጋለች። የበለጠ ልታውቀው ፈልጋለች። ከራሷም የሸሸገችውን ነገር አስቀድሞ ከእርሱ ጋር ተጋርታለች።ዝግ ሆኖ ለአመታት የቆየውን የሕይወቷ ክፍል ውስጥ ቀስ በቀስ ቢሆንም እያስገባችው ነው።እንደገና እንዲስማት ፈቅዳለት ነበር። እና እንደገና ልትስመው ፈለገች።እና ወደ እሷ ሲጠጋ፣ ልቧ ተናወጠ እና በጉጉት ቀዘቀዘ።
‹‹ደግመህ ልታደርገው ነው?.››አይኖቹ መንገዳቸውን እየተከተሉ ነው።
‹‹ ደጋግሜ ከማድረግ ውጭ ምርጫ የለኝም….የሚጠገብ አይነት ነገር አይደለም...››አላት
‹‹እሺ እንደፈለክ››አለችና ደረቱ ላይ ተለጠፈችበት፡፡
‹‹ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ እንደማያውቅ አውቃለሁ። ይህ ሊሆን ይችላል ብዬ አላሰብኩም ነበር።››የተስፋውን ቃል በቃሉ ሰማች።
ቀጠለ‹‹መጀመሪያ ስታገኚኝ የወደድሺኝ አይመስለኝም ነበር›› አላት
‹‹በሞተር ሳይክል ስለነበርክ ነው››
ጣቶቹን በፀጉሯ ውስጥ ተርመሰመሰ፣ ማዕበላቸውን አስተካክሎ፣ ብርሃን በመላ ሰውነታቸው እየተንቦገቦገ ነው ።በሌላ ሰው እጅ ቁጥጥር ስር በገመድ ላይ እንዳለ ካይት በቀስታ ወደ ላይ የምትንሳፈፍ አይነት ስሜት ተሰማት። ሆኖም በተመሳሳይ ጊዜ፣ በህይወቷ ውስጥ ሌላ ሰው የማግኘት ተስፋው አስደሰታት።አሁን ያለፈ ህይወቷን ለመልቀቅ ዝግጁ ነበረች? በህይወቷ ውስጥ እሱን ሙሉ በሙሉ ለማሳተፍ ፍቃደኛ ሆናለች፡፡ሀሳቡ የጋለ ስሜት እና የፍርሃት ውህደት እንዲሰማት አደረጋት።አሁን በድጋሚ ብትስመው ምን ይሆናል?
‹‹ራሄል፣ እዚህ ነሽ?››የለሊሴን ድምፅ ከኩሽና ተጣራ፣ ራሄልን ወደ እውነታው ተመንጭቃ ተመለሰች።
ከተቀመጠችበት ተነሳችና ቆመች…ጎተተና እንደገና ሳማት።የወሰደው እርምጃ የራሄልን ልብ አቀለጠው። ራሷን በጣም ርቃ እንድትንሳፈፍ የፈቀደች ያህል ተሰማት። ስሜቶች ህይወቷን እንዲቆጣጠሩ ያደረጋትን ጠንካራ መሰረት ተቀብለዋለች።
‹‹አሁን መሄድ አለብኝ››
‹‹እሺ ሂጂ››
ራሄል ሁል ጊዜ ሰዎች በሚፈልጉበት መንገድ እንደማይሄዱ ታውቃለች። ኪሩቤል በአደጋ ሆስፒታል ገብቶ በህመም እየተሰቃየ ለሞት ሲያጣጥር ረጅም እና ጠንክራ ፀሎት ስትጸልይ ነበር። አሁንም ግን በእግዚአብሔር ለመታመን ዝግጁ መሆኗን እርግጠኛ አልነበረችም።
‹‹ደስተኛ መሆን የሚገባኝ ይመስለኛል››ስትል ለራሷ አጉተመተመች፡፡
በዚህ ግንኙነታቸው ውስጥ እሷ እየመራችው እንደሆነ ተሰምቷታል, ግን በተመሳሳይ ጊዜ ስለ ስሜቷ እርግጠኛ አልነበረችም. ምን ማድረግ እንዳለባትም እርግጠኛ አይደለችም. እንደገና ራሷን ለጥቃት የተጋለጠች ለማድረግ እንደደፈረች አላወቀችም።እሱ ጥሩ ….ደግ እና ጨዋ ነበር። እና ባየችው ቁጥር ለእሱ ያላት ስሜት እየጠነከረ ነው የሄደው። በህይወቷ ውስጥ የት እንደምታስቀምጠው ለማወቅ ትንሽ ጊዜ ያስፈልጋታል።
‹‹ታውቃለህ አይደል..እንደዚህ ማድረግ አልነበረብንም››አለችው….አንደበቷ ከልቧ ተቃራኒ የሆኑ ቃላቶቸን ነው ያወጣው፡፡ ሃሳቧን ቀይራ መልሳ ደረቱ ላይ ከመለጠፏ በፊት ‹‹እዚህ ነኝ ለሊሴ››እያለች ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
ኤልያስ እጆቹን ዝቅ አደረገ…ተወጣትሮ የነበረው ስሜቱ ተኮመታተረ፡፡የብቸኝነት ማዕበል ሲያናውፀው ተሰማው ። ምን አድርጋው እንደሄደች አላወቀም…ብቻ የሆነ የአካሉን ክፍል ቦጭቃ ከራሷ ጋር ይዛ እንደሄደች ነው የተሰማው ፡፡ደግሞ በተመሳሳይ ከተሰቀለበት ማማ ገፍትራ ወደገደል ውስጥ ጨምራው ነው የሄደችው፡፡ ቀስ አለና ማንም ሳያየው ሹክክ ብሎ ወጣ…ቀጥ ብሎ ወደቤቱ ነው የሄደው፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ቢንያም እና ዔሊያስ አዲሱ ቤት ውስጥ ሆነው አንዳንድ ነገሮችን እያስተካከሉ ነው፡፡
‹‹እነዚህ ክፍሎች ከተጠናቀቁ በኋላ የሚቀጥለው ፕሮጀክት የሳሎኑን ሴራሚክ ማሰራት ነው›› አለ ዔሊ፡፡
ቢኒያምም ‹‹አዎ..እኔም እንደዛ ነው ያሰብኩት ››ሲል ለሀሳቡ ድጋፍ ሰጠው፡፡
‹‹ሰሞኑን በቤቱ የፊኒሽንግ ስራ ላይ ያለህ ትኩረትና ጉጉት ጨምሮብኛል ..ምነው ?ጉዳዩ ከራሄል ጋር የሚያገናኘው ነገር አለው እንዴ?››ሲል ጠየቀው፡፡
ዔሊያስ የሚናገረው ማንኛውም ነገር በወንድሙ በተሳሳተ መንገድ እንደሚተረጎምበት ስለሚያውቅ ዝም ለማለት ወሰነ ። የቀረውን የእንጨት ፍቅፋቂ ጠራርጎ ቆሻሻ መጣያ ውስጥ ጣላው፡፡
ቢኒያም ወደሌላ ተያያዥ ጥያቄ ተሸጋገረ‹‹በቤተሰቧቾ ግቢ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢ አመታዊ ዝግጅት ላይ ቆንጆዎቹ ጥንዶች እናንተ እንደነበራችሁ ሰምቻለሁ።››
‹‹ስለ ቆንጆው ክፍል አላውቅም, ግን አዎ አብረን ጠቃሚ የሚባል ጊዜ አሳልፈናል.››ሲል መለሰለት፡፡
ቢኒያም መሳሪያዎቹን እየሰበሰበ ‹‹እሷ በጣም የምትስብ ሴት ነች፣ አይመስልህም?›› ሲል አከለበት።
ዔሊያስ ሳጥኑን አነሳና‹‹በአሁኑ ጊዜ ስለእሷ ምንም ላለማሰብ እሞክራለሁ…ካለበለዚያ ችግር ውስጥ ያስገባኛል.››ሲል መለሰለት ።
የሚናገረው ነገር ሙሉ በሙሉ እውነት አልነበረም። ከዝግጅቱ ቀን ጀምሮ፣ ብዙ ነገሮችን ከአእምሮው ማውጣት አልቻለም። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እዛው በራሄል ቢሮ ውስጥ፣ ወደ ኋላ የተገፋ.. የተተወ ያህል ተሰምቶታል። በቀጣዮቹ ቀናት ብዙ ጊዜ፣ ወደቤቷ ተንደርድሮ ለመሄድ ስሜቱ ተፈትኗት ነበር።እሱ ግን እንደምንም ተቋቁሞት እራሱን አቅቧል። ለራሄል ልቡን ከፍቶ ነበር፣ እሷም እንዲሁ ያደረገች መስሎት ነበር። ከዚያ በኋላ ግን ስለእሷ ያለውን ስሜት በትክክል ሲነግራት.. ቀዝቀዝ አድርጋዋለች።‹‹እንደዛ ማድረግ ያለብን አይመስለኝም።›› ነበር ያለችው….ታዲያ ለምን እንዲስማት ፈቀደችለት?እና ለምን አሁንም ስለ እሷ ያስባል? እሷን ከአእምሮው ለማስወጣት ወስኗል። እሱ ትኩረቱን የሚያሳርፍበት የሚሠራው ቤት ስላለው አመሰገነ። እንደ ሞኝ እሷ በቀደደችለት ቦይ ፈቃደኛ ሆኖ እንዲፈስ አድርጋዋለች።
‹‹እሷን እንደ ፍቅር ጓደኛ አድርጎ ማሰብ ከመጠን ያለፈ ነው›› አለ ፡፡
ቢንያም ‹‹ከየትኛውም ሴት ጋር ለተወሰነ ጊዜ አላሳለፍክም። ይህችኛዋ የተለየ ምን አላት?››
ዔሊያስ ሱሪው ላይ ያለውን አቧራ ጠርጎ አራገፈው። ‹‹ እርግጠኛ አይደለሁም።››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹ወደሀታል?››
ኤሊያስ ቅንነት በጎደለው እንቅስቃሴ እጁን አወዛወዘ። እሱ ካልወደዳት ለምን አብዝቶ ስለእሷ ያስባል ?‹‹የሆነ ሆኖ ..ለጊዜያዊ ስሜት እንዳልፈለኳት አውቃለሁ››
ቢንያም ቀጠለ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ማውራት ትፈልጋለህ?››
‹‹አይ ..ርዕስ ብንቀይር ደስ ይለኛል››አለው፡፡
ቢንያምን ወንድሙ ስሜት ተረዳና ርእሱን ቀየረ ‹‹በቀደም ለሆነ የስራ ጉዳይ…እኛ የነበርንበት የህፃናት የማደጎ ድርጅት ሄጄ ነበር ..አስተዳዳሪዋ ወይዘሪት ሜላት ስለአንተ ስትጠይቀኝ ነበር፡፡ሰሞኑን ፋይል ሲያደራጁ በአንተ ፋይል ላይ በፊት ካሳየችህ የተለየ ነገር እንዳገኘች ነገረችኝ፡፡››
ኤልያስ በሰማው ነገር ደነገጠ ‹‹ታዲያ ለምን አልነገርከኝም? ስለ ወላጆቼ የበለጠ ለማወቅ እንደምፈልግ ታውቃለህ።››
ቢንያም ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ምን እንደተሰማኝ ታውቃለህ.? አሳዳጊ ወላጇቼ የሚያስፈልገኝን ሁሉንም ነገር ነው የሰጡኝ … ስለ ወለደችኝ እናቴ ምንም ግድ የለኝም. አንተም ተመሳሳይ ነገር እንድታደርግ እመኛለሁ ምክንያቱም ወላጆችህ ሞተዋል..ተመልሰው አይመጡም ..በዚህ ጉዳይ ላይ አእምሮህን እንድትበጠብጥ አልፈልግም..ለዛነው ችላ ያልኩት››
ዔሊያስ በማደጎ ወንድሙ ላይ ያለው ብስጭት አደገ ‹‹የአንተ እናት ‹መቼም ቢሆን ከልጄ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ለማድረግ አልሞክርም› የሚል ስምምነት ፈርመዋል።የገዛ የስጋ እናትህ መቼም ቢሆን ከአንተ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዲኖራት አልፈለገችም…. የእኔ ግን የተለየ ነው … የወላጆቼ ትዝታዎች በልቤ ውስጥ ናቸው… ምንም እንኳን አንተም ሆንክ አሳዳጊ ወላጆቻቼ ስለ ወላጆቼ በጭራሽ እንዳውቅ ባትፈቅዱልኝም…..እኔ ግን ፍለጋዬን አላቆምም.››ሲል በቁጣ ተንዘረዘረበት፡፡
ቢኒያም በስክነት ‹‹ ብቻ እንደወንድምነቴ የተሰማኝን ነገሬሀለው….››አለው፡፡
ኤሊያስ ምንም መልስ አልሰጠውም ። እሱ እና ቢንያምን ከዚህ በፊት በዚህ ጉዳይ ላይ በተደጋጋሚ ተወያይተው ነበር ግን አንድም ቀን አንድ አይነት አቋም አራምደው አያውቁም። እሱ አሳዳጊዎቹ ከማደጎ ቤት ከተቀበሉት በኋላ በእውነት የቤተሰቡ አካል እንደሆነ ለማመን ብዙ አመታት ፈጅቶበት ነበር፣ እና ከዛም የገዛ ወላጆቹ እና የእነሱ አሳዛኝ ሞት ትዝታዎች ብዙውን ጊዜ ጣልቃ በመግባት በእሱና በአሳዳጊ ወላጆቹ መካከል ክፍተት እንደፈጠረ ነበር፡፡
‹‹ስለ መዛግብት ስላልነገርኩህ ይቅርታ… አስፈላጊ ነው ብዬ አላሰብኩም ነበር. ከዚህ ሁሉ በላይ የሆንክ መስሎኝ ነበር.››
ኤልያስ በሀሳብ ነሆለለ።የሚወዳት ልጅ ራሔል ትዝ አለችው፡፡እሷ በሁለቱም በኩል ወደ ኋላ ዞራ የትውልድ ሀረጓን በኩራት መዘርዘር ትችላለች…ከዛም አልፎ በእናቷ የዘር ግንድ ሔዶ ሄዶ ከሰለሞን ዘር ይመዘዛል ብለው እናቷ ነገረውታል…. በዚህም ምክንያት እሷ በተጠየቀች ቁጥር ከየት እንደመጣች ለሰዎች በኩራት መንገር ትችላለች። እሱ ግን የዘር ግንዱ በአጭሩ ብጥስ ብሎ መጥፋቱ ከሌሎች ሰዎች ያነሰ እንደሆነ እንዲሰማው አድርጎታል።አሳዳጊ ወላጆቹን ይወዳቸዋል ። በወጣትነት ዘመናቸው ወደቤታቸው ወስደው… አመፁን እና አስቸጋሪ ፀባዩን ተቋቁመው በፍቅር አሳድገውታል..አሁንም ድረስ ስለእሱ ማሰብና እሱን ከመንከባከብ ሲደክማቸው አይቶ አያውቅም።ልክ እንደእነሱ አማኝ ሆኖ ወደ ቤተ ክርስቲያን መመላለስ አለመቻሉ እንዴት እንዳሰቃያቸው ያውቃል።ግን በተመሳሳይ ስለስጋ ወላጆቹ ያለውን ቁርጥራጭ ትውስታዎቹን ማጥፋት አልቻለም. ….አልፈለገምም ነበር።
ከረጅም ዝምታ በኋላ ቢኒያም ‹‹ኤሊያስ ልነግርህ የምችለው ነገር የበለጠ ማወቅ ከፈለግክ ከወይዘሪት ሜላት ጋር ሄደህ ራስህ ብትነጋገር ጥሩ ይመስለኛል››የሚል ሀሳብ አቀረበለት፡፡
ዠቨ
‹‹እንደዚያ የማደርግ ይመስለኛል›› አለ.
ዶ/ር ኤልያስ በማግስቱ አስረአንድ ሰዓት ላይ በህፃናት ማሳደጊያ በጎ አድርጎት ድርጅት ቢሮ ውስጥ ከመዘጋቱ በፊት ተገኘው። ምሳ ሰዓት ላይ ስልክ ደውሎ ቀጠሮ ይዞ ነበር ። ወ.ሪት ሜሮን ተከትሎ ወደ ቢሮዋ ሲገባ ልቡ ከተገቢው በላይ እየመታ ነበር።
የራሄል ምስል በአእምሮው ውስጥ ድቅን አለና ለስለስ ያለ ህመም ተሰማው። ‹‹ ዶ/ር ኤልያስ…እንኳን በሰላም መጣህ…ምን እንድረዳህ ትፈልጋለህ?›› ስትል ጠየቀችው ፡፡
‹‹ስለ ስጋ ወላጆቼ አንዳንድ ነገሮች ሚያስረዳ ፋይል እንዳለሽ ተረድቻለሁ›› አለ ።ወ.ሪት ሜላት ጭንቅላቷን በአውንታ ነቀነቀች። ‹‹ብዙ መረጃ አልያዘም ነገር ግን ጥቂትም ቢሆን ምን አልባት የምትፈልገውን ነገር ልታገኝበት ትችል ይሆናል::››
‹‹እና አሁን ማየት ብችል ደስ ይለኛል?››
‹‹እላይ ፎቅ ላይ በሚገኝ መዝገብ ቤት ውስጥ ነው ያለው…ትንሽ ታገሰኝ ይዤ ልምጣ ›› ብላ እዛው የተቀመጠበት ትታው ወጥታ ሄደች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ቢንያም እና ዔሊያስ አዲሱ ቤት ውስጥ ሆነው አንዳንድ ነገሮችን እያስተካከሉ ነው፡፡
‹‹እነዚህ ክፍሎች ከተጠናቀቁ በኋላ የሚቀጥለው ፕሮጀክት የሳሎኑን ሴራሚክ ማሰራት ነው›› አለ ዔሊ፡፡
ቢኒያምም ‹‹አዎ..እኔም እንደዛ ነው ያሰብኩት ››ሲል ለሀሳቡ ድጋፍ ሰጠው፡፡
‹‹ሰሞኑን በቤቱ የፊኒሽንግ ስራ ላይ ያለህ ትኩረትና ጉጉት ጨምሮብኛል ..ምነው ?ጉዳዩ ከራሄል ጋር የሚያገናኘው ነገር አለው እንዴ?››ሲል ጠየቀው፡፡
ዔሊያስ የሚናገረው ማንኛውም ነገር በወንድሙ በተሳሳተ መንገድ እንደሚተረጎምበት ስለሚያውቅ ዝም ለማለት ወሰነ ። የቀረውን የእንጨት ፍቅፋቂ ጠራርጎ ቆሻሻ መጣያ ውስጥ ጣላው፡፡
ቢኒያም ወደሌላ ተያያዥ ጥያቄ ተሸጋገረ‹‹በቤተሰቧቾ ግቢ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢ አመታዊ ዝግጅት ላይ ቆንጆዎቹ ጥንዶች እናንተ እንደነበራችሁ ሰምቻለሁ።››
‹‹ስለ ቆንጆው ክፍል አላውቅም, ግን አዎ አብረን ጠቃሚ የሚባል ጊዜ አሳልፈናል.››ሲል መለሰለት፡፡
ቢኒያም መሳሪያዎቹን እየሰበሰበ ‹‹እሷ በጣም የምትስብ ሴት ነች፣ አይመስልህም?›› ሲል አከለበት።
ዔሊያስ ሳጥኑን አነሳና‹‹በአሁኑ ጊዜ ስለእሷ ምንም ላለማሰብ እሞክራለሁ…ካለበለዚያ ችግር ውስጥ ያስገባኛል.››ሲል መለሰለት ።
የሚናገረው ነገር ሙሉ በሙሉ እውነት አልነበረም። ከዝግጅቱ ቀን ጀምሮ፣ ብዙ ነገሮችን ከአእምሮው ማውጣት አልቻለም። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እዛው በራሄል ቢሮ ውስጥ፣ ወደ ኋላ የተገፋ.. የተተወ ያህል ተሰምቶታል። በቀጣዮቹ ቀናት ብዙ ጊዜ፣ ወደቤቷ ተንደርድሮ ለመሄድ ስሜቱ ተፈትኗት ነበር።እሱ ግን እንደምንም ተቋቁሞት እራሱን አቅቧል። ለራሄል ልቡን ከፍቶ ነበር፣ እሷም እንዲሁ ያደረገች መስሎት ነበር። ከዚያ በኋላ ግን ስለእሷ ያለውን ስሜት በትክክል ሲነግራት.. ቀዝቀዝ አድርጋዋለች።‹‹እንደዛ ማድረግ ያለብን አይመስለኝም።›› ነበር ያለችው….ታዲያ ለምን እንዲስማት ፈቀደችለት?እና ለምን አሁንም ስለ እሷ ያስባል? እሷን ከአእምሮው ለማስወጣት ወስኗል። እሱ ትኩረቱን የሚያሳርፍበት የሚሠራው ቤት ስላለው አመሰገነ። እንደ ሞኝ እሷ በቀደደችለት ቦይ ፈቃደኛ ሆኖ እንዲፈስ አድርጋዋለች።
‹‹እሷን እንደ ፍቅር ጓደኛ አድርጎ ማሰብ ከመጠን ያለፈ ነው›› አለ ፡፡
ቢንያም ‹‹ከየትኛውም ሴት ጋር ለተወሰነ ጊዜ አላሳለፍክም። ይህችኛዋ የተለየ ምን አላት?››
ዔሊያስ ሱሪው ላይ ያለውን አቧራ ጠርጎ አራገፈው። ‹‹ እርግጠኛ አይደለሁም።››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹ወደሀታል?››
ኤሊያስ ቅንነት በጎደለው እንቅስቃሴ እጁን አወዛወዘ። እሱ ካልወደዳት ለምን አብዝቶ ስለእሷ ያስባል ?‹‹የሆነ ሆኖ ..ለጊዜያዊ ስሜት እንዳልፈለኳት አውቃለሁ››
ቢንያም ቀጠለ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ማውራት ትፈልጋለህ?››
‹‹አይ ..ርዕስ ብንቀይር ደስ ይለኛል››አለው፡፡
ቢንያምን ወንድሙ ስሜት ተረዳና ርእሱን ቀየረ ‹‹በቀደም ለሆነ የስራ ጉዳይ…እኛ የነበርንበት የህፃናት የማደጎ ድርጅት ሄጄ ነበር ..አስተዳዳሪዋ ወይዘሪት ሜላት ስለአንተ ስትጠይቀኝ ነበር፡፡ሰሞኑን ፋይል ሲያደራጁ በአንተ ፋይል ላይ በፊት ካሳየችህ የተለየ ነገር እንዳገኘች ነገረችኝ፡፡››
ኤልያስ በሰማው ነገር ደነገጠ ‹‹ታዲያ ለምን አልነገርከኝም? ስለ ወላጆቼ የበለጠ ለማወቅ እንደምፈልግ ታውቃለህ።››
ቢንያም ‹‹ስለዚህ ጉዳይ ምን እንደተሰማኝ ታውቃለህ.? አሳዳጊ ወላጇቼ የሚያስፈልገኝን ሁሉንም ነገር ነው የሰጡኝ … ስለ ወለደችኝ እናቴ ምንም ግድ የለኝም. አንተም ተመሳሳይ ነገር እንድታደርግ እመኛለሁ ምክንያቱም ወላጆችህ ሞተዋል..ተመልሰው አይመጡም ..በዚህ ጉዳይ ላይ አእምሮህን እንድትበጠብጥ አልፈልግም..ለዛነው ችላ ያልኩት››
ዔሊያስ በማደጎ ወንድሙ ላይ ያለው ብስጭት አደገ ‹‹የአንተ እናት ‹መቼም ቢሆን ከልጄ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ለማድረግ አልሞክርም› የሚል ስምምነት ፈርመዋል።የገዛ የስጋ እናትህ መቼም ቢሆን ከአንተ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዲኖራት አልፈለገችም…. የእኔ ግን የተለየ ነው … የወላጆቼ ትዝታዎች በልቤ ውስጥ ናቸው… ምንም እንኳን አንተም ሆንክ አሳዳጊ ወላጆቻቼ ስለ ወላጆቼ በጭራሽ እንዳውቅ ባትፈቅዱልኝም…..እኔ ግን ፍለጋዬን አላቆምም.››ሲል በቁጣ ተንዘረዘረበት፡፡
ቢኒያም በስክነት ‹‹ ብቻ እንደወንድምነቴ የተሰማኝን ነገሬሀለው….››አለው፡፡
ኤሊያስ ምንም መልስ አልሰጠውም ። እሱ እና ቢንያምን ከዚህ በፊት በዚህ ጉዳይ ላይ በተደጋጋሚ ተወያይተው ነበር ግን አንድም ቀን አንድ አይነት አቋም አራምደው አያውቁም። እሱ አሳዳጊዎቹ ከማደጎ ቤት ከተቀበሉት በኋላ በእውነት የቤተሰቡ አካል እንደሆነ ለማመን ብዙ አመታት ፈጅቶበት ነበር፣ እና ከዛም የገዛ ወላጆቹ እና የእነሱ አሳዛኝ ሞት ትዝታዎች ብዙውን ጊዜ ጣልቃ በመግባት በእሱና በአሳዳጊ ወላጆቹ መካከል ክፍተት እንደፈጠረ ነበር፡፡
‹‹ስለ መዛግብት ስላልነገርኩህ ይቅርታ… አስፈላጊ ነው ብዬ አላሰብኩም ነበር. ከዚህ ሁሉ በላይ የሆንክ መስሎኝ ነበር.››
ኤልያስ በሀሳብ ነሆለለ።የሚወዳት ልጅ ራሔል ትዝ አለችው፡፡እሷ በሁለቱም በኩል ወደ ኋላ ዞራ የትውልድ ሀረጓን በኩራት መዘርዘር ትችላለች…ከዛም አልፎ በእናቷ የዘር ግንድ ሔዶ ሄዶ ከሰለሞን ዘር ይመዘዛል ብለው እናቷ ነገረውታል…. በዚህም ምክንያት እሷ በተጠየቀች ቁጥር ከየት እንደመጣች ለሰዎች በኩራት መንገር ትችላለች። እሱ ግን የዘር ግንዱ በአጭሩ ብጥስ ብሎ መጥፋቱ ከሌሎች ሰዎች ያነሰ እንደሆነ እንዲሰማው አድርጎታል።አሳዳጊ ወላጆቹን ይወዳቸዋል ። በወጣትነት ዘመናቸው ወደቤታቸው ወስደው… አመፁን እና አስቸጋሪ ፀባዩን ተቋቁመው በፍቅር አሳድገውታል..አሁንም ድረስ ስለእሱ ማሰብና እሱን ከመንከባከብ ሲደክማቸው አይቶ አያውቅም።ልክ እንደእነሱ አማኝ ሆኖ ወደ ቤተ ክርስቲያን መመላለስ አለመቻሉ እንዴት እንዳሰቃያቸው ያውቃል።ግን በተመሳሳይ ስለስጋ ወላጆቹ ያለውን ቁርጥራጭ ትውስታዎቹን ማጥፋት አልቻለም. ….አልፈለገምም ነበር።
ከረጅም ዝምታ በኋላ ቢኒያም ‹‹ኤሊያስ ልነግርህ የምችለው ነገር የበለጠ ማወቅ ከፈለግክ ከወይዘሪት ሜላት ጋር ሄደህ ራስህ ብትነጋገር ጥሩ ይመስለኛል››የሚል ሀሳብ አቀረበለት፡፡
ዠቨ
‹‹እንደዚያ የማደርግ ይመስለኛል›› አለ.
ዶ/ር ኤልያስ በማግስቱ አስረአንድ ሰዓት ላይ በህፃናት ማሳደጊያ በጎ አድርጎት ድርጅት ቢሮ ውስጥ ከመዘጋቱ በፊት ተገኘው። ምሳ ሰዓት ላይ ስልክ ደውሎ ቀጠሮ ይዞ ነበር ። ወ.ሪት ሜሮን ተከትሎ ወደ ቢሮዋ ሲገባ ልቡ ከተገቢው በላይ እየመታ ነበር።
የራሄል ምስል በአእምሮው ውስጥ ድቅን አለና ለስለስ ያለ ህመም ተሰማው። ‹‹ ዶ/ር ኤልያስ…እንኳን በሰላም መጣህ…ምን እንድረዳህ ትፈልጋለህ?›› ስትል ጠየቀችው ፡፡
‹‹ስለ ስጋ ወላጆቼ አንዳንድ ነገሮች ሚያስረዳ ፋይል እንዳለሽ ተረድቻለሁ›› አለ ።ወ.ሪት ሜላት ጭንቅላቷን በአውንታ ነቀነቀች። ‹‹ብዙ መረጃ አልያዘም ነገር ግን ጥቂትም ቢሆን ምን አልባት የምትፈልገውን ነገር ልታገኝበት ትችል ይሆናል::››
‹‹እና አሁን ማየት ብችል ደስ ይለኛል?››
‹‹እላይ ፎቅ ላይ በሚገኝ መዝገብ ቤት ውስጥ ነው ያለው…ትንሽ ታገሰኝ ይዤ ልምጣ ›› ብላ እዛው የተቀመጠበት ትታው ወጥታ ሄደች፡፡
ኤሊያስ ለአፍታ ተስፋ መቁረጥ ተሰማው። ከዚህ በፊት የወላጆቹን ፎቶዎችን ካገኘ በኋላ ከእሱ የተደበቁ ብዙ መረጃዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ተስፋ አድርጓል ። ልክ እንደሌሎች ልጆች፣ወላጆቹ ሲሞቱ ከፊል የህይወቱ ክፍል እንደተወሰደበት ሆኖ ተሰምቶት ነበር። ስለእነሱ ተጨማሪ መረጃ ማወቁ.. ትዝታቸውን ለእርሱ የበለጠ እውን ያደርጋለታል።
ወ.ሪት ሜሮን ፋይሉን ይዛ መጣችና እንዲመለከታቸው ከሰጠችው በኋላ ወደ መቀመጫዋ ሄዳ ተቀመጠች፡፡
‹‹ወደ ቤት ልወስደው እችላለሁ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ፋይልህ ባይታሸግም ከቢሮው እንዲወጡ አንፈቅድም ፣ ግን ኮፒውን ላዘጋጅልህ እችላለው››አለችውና ፋይሉን ከእጁ ተቀብላ መልሳ ወጥታ ሄደች፡፡
ኤሊያስ ፊት ለፊት ግድግዳው ላይ በተርታ የተሰቀለ የሕጻናት እና የትንሽ ልጆች ምስሎች ተመለከተ። አንዳንዶቹ ደብዝዘው ነበር፣ ግልፅ የሆነለት እሷ ስልጣን ከመውሰዷ በፊት ከነበረው ጊዜ ጀምሮ በበጎአድራጎት ድርጅቱ ውስጥ ያለፉትን ህፃናትን ብቻ የሚያካትት ነበር። በዚህ ግድግዳ ላይ የእሱ እና የቢንያም ምስል ታይቶ ይታውቅ እንደሆነ አሰበ፡፡ከአምስት ደቂቃ በኋላ ፋይሉን በካኪ ፖስታ ይዛ ተመለሰች። ‹‹ሁሉንም መረጃ እዚያ ውስጥ ጨምሬልሀለው. ሁሉንም ነገር እንዳገኘህ ለማረጋገጥ ከፈለክ ዳግመኛ ከመጀመሪያው የፋይል ይዘቶች ጋር ልናወዳድረው እንችላለን.››
ኤሊያስ ኤንቨሎፑን ተቀበለና ‹‹ግድ የለም…ቤት ወስጄ ብመለከተው እመርጣለሁ‹›› አላት ፡፡በእጁ የያዘው ፋይል በጣም ቀላል ሆኖ ተሰማው፤የህይወቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት ታሪክን እንደማይመጥን ተሰማው፡፡ ‹‹ለዚህ አመሰግናለሁ, ብድር መላሽ ያድርገኝ.››ብሎ ቢሮዋን ለቆ ወጣ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ወ.ሪት ሜሮን ፋይሉን ይዛ መጣችና እንዲመለከታቸው ከሰጠችው በኋላ ወደ መቀመጫዋ ሄዳ ተቀመጠች፡፡
‹‹ወደ ቤት ልወስደው እችላለሁ?››ሲል ጠየቃት
‹‹ፋይልህ ባይታሸግም ከቢሮው እንዲወጡ አንፈቅድም ፣ ግን ኮፒውን ላዘጋጅልህ እችላለው››አለችውና ፋይሉን ከእጁ ተቀብላ መልሳ ወጥታ ሄደች፡፡
ኤሊያስ ፊት ለፊት ግድግዳው ላይ በተርታ የተሰቀለ የሕጻናት እና የትንሽ ልጆች ምስሎች ተመለከተ። አንዳንዶቹ ደብዝዘው ነበር፣ ግልፅ የሆነለት እሷ ስልጣን ከመውሰዷ በፊት ከነበረው ጊዜ ጀምሮ በበጎአድራጎት ድርጅቱ ውስጥ ያለፉትን ህፃናትን ብቻ የሚያካትት ነበር። በዚህ ግድግዳ ላይ የእሱ እና የቢንያም ምስል ታይቶ ይታውቅ እንደሆነ አሰበ፡፡ከአምስት ደቂቃ በኋላ ፋይሉን በካኪ ፖስታ ይዛ ተመለሰች። ‹‹ሁሉንም መረጃ እዚያ ውስጥ ጨምሬልሀለው. ሁሉንም ነገር እንዳገኘህ ለማረጋገጥ ከፈለክ ዳግመኛ ከመጀመሪያው የፋይል ይዘቶች ጋር ልናወዳድረው እንችላለን.››
ኤሊያስ ኤንቨሎፑን ተቀበለና ‹‹ግድ የለም…ቤት ወስጄ ብመለከተው እመርጣለሁ‹›› አላት ፡፡በእጁ የያዘው ፋይል በጣም ቀላል ሆኖ ተሰማው፤የህይወቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ዓመታት ታሪክን እንደማይመጥን ተሰማው፡፡ ‹‹ለዚህ አመሰግናለሁ, ብድር መላሽ ያድርገኝ.››ብሎ ቢሮዋን ለቆ ወጣ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
Forwarded from ምርጥ ቻናሎች ዲስክ