#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሰባት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ሙታኑን_ስቀብር
፡
፡
‹‹ወላጆችሽ የት ነው የሚኖሩት?›› ይህ ጥያቄ በተመድ ሥራዬን ከጀመርኩ ከጥቂት ወራት በኋላ የቀረበልኝ፡፡
‹‹ልቤ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር በሕይወት የሉም›› በማለት በትዕግሥት መለስኩ፡፡
‹‹በዘር ፍጅቱ ተገድለዋል፡፡››
የተመድ ሰቆቃዬን ለመርሳት የምችልበት ስፍራ አይደለም፡፡ እዚያ የሚሰሩት አብዛኞቹ ከሀገሪቱ ውጪ የመጡ ስለሆኑ የቤተሰቤን ዕጣ ፈንታ ሲያውቁ የዘውጌ አባላት አብዛኞቹ በተገደሉበት ሁኔታ እኔ እንዴት ልተርፍ አንደቻልኩ ለማወቅ በጣም ይጓጓሉ፡፡
‹‹ይቅርታ›› አሉኝ እያዋሩኝ ያሉት ሰውዬ፡፡ ‹‹አላወቅሁም፡፡ እንዳላበሳጨሁሽ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡›› ስማቸው ኮሎኔል ጉዬ ሲሆን ወደ ሩዋንዳ አገሪቱን በማረጋጋቱ ተግባር ለማገዝ የመጣው የተመድ ሰላም አስከባሪ ጦር አዛዥ ሴኔጋላዊ ናቸው፡፡ እኔን ስለማበሳጨት እንዳይጨነቁ ለኮሎኔሉ ነገርኳቸው፡፡ ጥያቄ መጠየቅ ያለፍኩትን ሁሉ ከግምት ውስጥ ሳስገባው ከሚያሳስቡኝ ነገሮች በጣም ዝቅተኛውን ደረጃ ነው የሚይዘው፡፡ አሁንም ቢሆን ከጦርነቱ ወዲህ ባላያቸውም አክስቶችና በመጣሁበት ኪቡዬ ክፍለሀገር የሚኖር አጎት እንዳለኝ አሳወቅኋቸው፡፡
‹‹አሃ፣ ኪቡዬ … እዚያ የሰፈሩ የተወሰኑ ወታደሮች አሉኝ›› በማለት መለሱልኝ፡፡ ‹‹ዘመዶችሽን መጠየቅ ካስፈለገሽ ላጓጉዝሽና ራሴ ላጅብሽ እችላለሁ፡፡ ጓደኛም ከፈልግሽ ማምጣት ትችያለሽ፡፡››
በሀገሪቱ መዘዋወር ያን ጊዜም ቢሆን አስቸጋሪና አደጋ ላይ የሚጥል ስለሆነ የእርሳቸው ግብዣ ትልቅ ችሮታ ነው፡፡
‹‹በእውነት? መቼ እንደሆነ ይንገሩኝና እንሄዳለን ኮሎኔል፡፡›› ከሁለት ሳምንታት በኋላ ሳራና እኔ ወታደራዊ ጠያራ ላይ በቀበቶ ታስረን አንዳችን የሌላችንን እጆች እየያዝንና በደስታ እየሣቅን በሩዋንዳ አረንጓዴ ተራሮች ላይ እንበር ጀመር፡፡ ሁለታችንም በአየር በርረን ስለማናውቅ ኮሎኔሉ የመብረር እድሉን ሲሰጡን እውነት አልመሰለንም ነበር!
ውቧን አገሬን ቁልቁል ሳያት የዘር ጭፍጨፋውን አስቀያሚ እውነታ ማመን አስቸገረኝ፡፡ በነዚያ ጨለማ ቀናት ምን ያህል ጊዜ ነው ወፍ ሆኜ በተወለድኩ ብዬ የተመኘሁት? ምን ያህልስ ጊዜ ነው ከመታጠቢያ ቤት እስር ቤቴ ወጥቼ ከአሰቃቂው ሰቆቃ በላይ ርቄ መብረርን ያለምኩት? እና አሁን እዚህ ወንጀሉ የተፈጸመበትን ስፍራ ተመልሼ ለመጎብኘት ይኸው እበር ይዣለሁ፡፡ ከማታባ አምልጬ ኪጋሊ ለመድረስ ስንት ጊዜ ፈጅቶብኝ እንደነበር አውርቼልዎታለሁ - ለመመለስ ይኸው 30 ደቂቃ ብቻ ፈጀብኝና አረፈው፡፡
ኤይማብል ከኔ ጋር ቢሆን ብዬ ተመኘሁ፤ ግን አልተቻለም፡፡ የመልዕክት መላላኪያ አገልግሎቱ ገና ቀርፋፋ ሲሆን፤ በዚያም ላይ ከእርሱ የመልስ ደብዳቤ እንኳን ለማግኘት ሳምንታት ፈጅቶብኛል፡፡ ከኔ ይህ ደብዳቤ ስለደረሰውና በሕይወት መኖሬን በማወቁ በጣም ደስተኛ ስለሆነ ስሜቱን ለመግለጽ ቃላት ሊያገኝልኝ እንዳልቻለ ገልጾ ጻፈልኝ፡፡ በዘር ፍጅቱ ወቅት የዜና ዘገባዎችን ይከታተል ስለነበር ሁሉም የቤተሰባችን አባል ከሌላው ሩዋንዳ ውስጥ ካለ ሁሉም ቱትሲ ጋር ወድሟል ብሎ አምኖ ተስፋ ቆርጦ ነበር፡፡ ለመገደል ካልሆነ በቀር በዘር ፍጅቱ ወቅት ወደ ሀገሪቱ የሚመለስበት ምንም መንገድ አልነበረውም፡፡
ለመምጣት ችግር የሆነበት ደግሞ በወቅቱ ለመመለስ ወጪውን መሸፈን አለመቻሉ ነው፡፡ ተማሪ ስለሆነ ገቢ የለውም፣ የሚኖረው 5 000 ኪሎሜትር ርቆ በሴኔጋል ነው፡፡ የአየር መሳፈሪያ ወጭው ብቻ 2 000 የአሜሪካን ዶላር ይፈጃል፤ ይህም የማይታሰብ ነው! ሙሉ ወጭውን ሸፍኖ የሚያስተምረው የአውሮፓ ድርጅትም ሩዋንዳ በጣም አደገኛ የጦርነት ቀጠና ስለሆነ ወደዚያ የምትሄድበትን ክፍያ አልከፍልልህም ይለዋል፡፡ ወንድሜ ትምህርቱን አቋርጦ መጥቶ ከኔ ጋር ለመኖር ቢፈልግም እማማንና አባባን የሚያኮራበት ሁነኛ መንገድ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት መጨረስ እንደሆነ ነገርኩት፡፡ በየሳምንቱ ለመጻጻፍ፣ ለወደፊቱ ለመጠያየቅና ገንዘብም ለማጠራቀም ተስማማን፡፡ እናም አሁን ወደ ማታባ ላገኘሁት የነጻ የአየር ጉዞ ምስጋና ይግባውና ቤታችንን ያለ ብቸኛው ቀሪ ወንድሜ እጎበኛለሁ፡፡
ትንሿ ወታደራዊ ጠያራ መሬት ላይ ካረፈች በኋላ ኮሎኔል ጉዬ ትራኦሬ ለሚባል ብርቱ ወጣት መኰንን አደራ ብለው በወታደሮቹ ምሽግ አስቀምጠውን ይሄዳሉ፡፡ እርሱም ለእያንዳንዱ ወታደር የኮሎኔል ጉዬ ልጆች ናቸው ብሎ አስተዋወቀን፡፡ ከዚህን ጊዜ በፊት በነበሩኝ የወታደር ምሽግ ቆይታዎቼ አግኝቼው የማላውቀውን አገኘሁ - ሳራና እኔ የየራሳችን ክፍል፣ የምንተኛባቸው አልጋዎች፣ ምርጥ ምግብ ብሎም የእያንዳንዱ ወታደር አክብሮትና እገዛ ተቸረን፡፡ እንዲያውም እስከ ንጋት ድረስ ባህላዊ የሴኔጋል ዘፈኖችን ሲዘፍኑና እርስ በርሳቸው ሲቀላለዱ አብረን አነጋን፡፡ ሳራ በአቀባበሉ ደስ ከመሰኘቷም በላይ ደኅንነት ሲሰማት እኔም አገሬ በመግባቴ ደስ ተሰኘሁ፡፡
በማግስቱ ወደ መንደሬ ለመሄድ ስምንት ኪሎሜትር የሚርቀውን የእግር መንገድ ለመጓዝ ስዘገጃጅ መኰንን ትራኦሬ ስለደህንነታችን ያለውን ሥጋት ይናገር ጀመር፡፡ የዘር ፍጅቱ ቢያበቃም በሀገሪቱ ግልጽ የሆነ ጥላቻ ስለነገሰ በዚያን ወቅትም ግድያ ይፈጸማል፡፡ መኰንኑ በትጥቅ አጀብ ሊልከን ወሰነ - አጀቡም ከሁለት ደርዘን ያላነሱ ወታደሮችንና አምስት ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችን ያጠቃልላል፡፡ ማታባ በጀግና ኩራት እንገባለን እንጂ እንደ ተመላሽ ስደተኛ አንሹለከለክም፡፡ በዚያች መንደር ያን ያህል ጊዜ በፍራቻና ሥጋት ተሸሽጌባታለሁ፤ አሁን ግን ራሴን ቀና አድርጌ መሄዴ መልካም ነው፡፡
በልጅነቴ በጣም በማውቀው ሰማይ ስር ተሸከርካሪዎቻችንን ስንነዳ ስሜቴ በፍጥነት ወደ ኃይለኛ ብስጭት ተለወጠ፡፡ ወንድሞቼና እኔ ብዙውን ጊዜ እንሄድበት ወደነበረው መንገድ ስንገባ ማልቀስ ጀመርኩ፤ ከዚያም በወቅቱ ጭር ባለው እናቴ ታስተምርበት በነበረው ትምህርት ቤት አልፈን አባታችንን ተከትለን በጠዋት ኪቩ ሐይቅ ወርደን ልንዋኝ በምናልፍበት መንገድ ቁልቁል ወረድን፡፡ ሳራ እጇን በትከሻዬ አድርጋ ልታጽናናኝ ብትሞክርም አልሆነም - መጽናናት የምችል አልነበርኩም፡፡ በፈራረሱ መስኮቶችና በተዘጉ የውጪ በሮች አጮልቀው የሚያዩን ፊቶች ጥላ ይታየኛል … ብዙ ወገኖቼን አሳደው የገደሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ፊቶች፡፡ ብዙዎቹን የቱትሲዎችን ቤቶች ራሳቸው ካቃጠሉ በኋላ አሁን ብቻቸውን ቆመው ያሉትን ብቸኛ ቤቶች በንብረትነት ይዘዋቸዋል፡፡ ከዚያም የራሴ ቤት ጋ ደረስን፡፡
ጣራ የለ፣ መስኮት የለ፣ በር የለ፤ ሙሉ በሙሉ ወድሟል፡፡ ገዳዮቹ ለጭፍጨፋቸው ሲዘገጃጁ እኛ ለቀናት ሬድዮ ስናዳምጥበት የነበረውን የተቃጠለውን መሬት የተወሰኑ ከፊል ግንቦች እየጠበቁት ዘብ ቆመዋል፡፡ አንድ ወቅት የወላጆቼ ሕልም የነበሩትን ባዶ ክፍሎች እየቃኘሁ በድንጋይ መዋቅሩ ውስጥ ተዟዟርኩ፡፡ የተጎዱ የቤት እቃዎችም ሆኑ የተቃጠሉ ልብሶች አሻራ የለም - ማንም ሊገምት እንደሚችለው ቤቱ ከመጋየቱ በፊት ንብረታችን ተዘርፏል፡፡
ብዙ በሕይወት የተረፉ ቱትሲ ጎረቤቶቻችን ወታደራዊ አጀባችንን አይተው ሰላም ሊሉኝ መጡ፡፡ በተደበቅኩባቸው ጊዜያት ስለተከሰቱት መጥፎ ነገሮች ነገሩኝ፤ እናቴ በተቀበረችበት ቦታ ላይ ሆነንም እምዬ እናቴ አንዴት እንደተገደለች ያስረዱኝ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሰባት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ሙታኑን_ስቀብር
፡
፡
‹‹ወላጆችሽ የት ነው የሚኖሩት?›› ይህ ጥያቄ በተመድ ሥራዬን ከጀመርኩ ከጥቂት ወራት በኋላ የቀረበልኝ፡፡
‹‹ልቤ ውስጥ ካልሆነ በስተቀር በሕይወት የሉም›› በማለት በትዕግሥት መለስኩ፡፡
‹‹በዘር ፍጅቱ ተገድለዋል፡፡››
የተመድ ሰቆቃዬን ለመርሳት የምችልበት ስፍራ አይደለም፡፡ እዚያ የሚሰሩት አብዛኞቹ ከሀገሪቱ ውጪ የመጡ ስለሆኑ የቤተሰቤን ዕጣ ፈንታ ሲያውቁ የዘውጌ አባላት አብዛኞቹ በተገደሉበት ሁኔታ እኔ እንዴት ልተርፍ አንደቻልኩ ለማወቅ በጣም ይጓጓሉ፡፡
‹‹ይቅርታ›› አሉኝ እያዋሩኝ ያሉት ሰውዬ፡፡ ‹‹አላወቅሁም፡፡ እንዳላበሳጨሁሽ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡›› ስማቸው ኮሎኔል ጉዬ ሲሆን ወደ ሩዋንዳ አገሪቱን በማረጋጋቱ ተግባር ለማገዝ የመጣው የተመድ ሰላም አስከባሪ ጦር አዛዥ ሴኔጋላዊ ናቸው፡፡ እኔን ስለማበሳጨት እንዳይጨነቁ ለኮሎኔሉ ነገርኳቸው፡፡ ጥያቄ መጠየቅ ያለፍኩትን ሁሉ ከግምት ውስጥ ሳስገባው ከሚያሳስቡኝ ነገሮች በጣም ዝቅተኛውን ደረጃ ነው የሚይዘው፡፡ አሁንም ቢሆን ከጦርነቱ ወዲህ ባላያቸውም አክስቶችና በመጣሁበት ኪቡዬ ክፍለሀገር የሚኖር አጎት እንዳለኝ አሳወቅኋቸው፡፡
‹‹አሃ፣ ኪቡዬ … እዚያ የሰፈሩ የተወሰኑ ወታደሮች አሉኝ›› በማለት መለሱልኝ፡፡ ‹‹ዘመዶችሽን መጠየቅ ካስፈለገሽ ላጓጉዝሽና ራሴ ላጅብሽ እችላለሁ፡፡ ጓደኛም ከፈልግሽ ማምጣት ትችያለሽ፡፡››
በሀገሪቱ መዘዋወር ያን ጊዜም ቢሆን አስቸጋሪና አደጋ ላይ የሚጥል ስለሆነ የእርሳቸው ግብዣ ትልቅ ችሮታ ነው፡፡
‹‹በእውነት? መቼ እንደሆነ ይንገሩኝና እንሄዳለን ኮሎኔል፡፡›› ከሁለት ሳምንታት በኋላ ሳራና እኔ ወታደራዊ ጠያራ ላይ በቀበቶ ታስረን አንዳችን የሌላችንን እጆች እየያዝንና በደስታ እየሣቅን በሩዋንዳ አረንጓዴ ተራሮች ላይ እንበር ጀመር፡፡ ሁለታችንም በአየር በርረን ስለማናውቅ ኮሎኔሉ የመብረር እድሉን ሲሰጡን እውነት አልመሰለንም ነበር!
ውቧን አገሬን ቁልቁል ሳያት የዘር ጭፍጨፋውን አስቀያሚ እውነታ ማመን አስቸገረኝ፡፡ በነዚያ ጨለማ ቀናት ምን ያህል ጊዜ ነው ወፍ ሆኜ በተወለድኩ ብዬ የተመኘሁት? ምን ያህልስ ጊዜ ነው ከመታጠቢያ ቤት እስር ቤቴ ወጥቼ ከአሰቃቂው ሰቆቃ በላይ ርቄ መብረርን ያለምኩት? እና አሁን እዚህ ወንጀሉ የተፈጸመበትን ስፍራ ተመልሼ ለመጎብኘት ይኸው እበር ይዣለሁ፡፡ ከማታባ አምልጬ ኪጋሊ ለመድረስ ስንት ጊዜ ፈጅቶብኝ እንደነበር አውርቼልዎታለሁ - ለመመለስ ይኸው 30 ደቂቃ ብቻ ፈጀብኝና አረፈው፡፡
ኤይማብል ከኔ ጋር ቢሆን ብዬ ተመኘሁ፤ ግን አልተቻለም፡፡ የመልዕክት መላላኪያ አገልግሎቱ ገና ቀርፋፋ ሲሆን፤ በዚያም ላይ ከእርሱ የመልስ ደብዳቤ እንኳን ለማግኘት ሳምንታት ፈጅቶብኛል፡፡ ከኔ ይህ ደብዳቤ ስለደረሰውና በሕይወት መኖሬን በማወቁ በጣም ደስተኛ ስለሆነ ስሜቱን ለመግለጽ ቃላት ሊያገኝልኝ እንዳልቻለ ገልጾ ጻፈልኝ፡፡ በዘር ፍጅቱ ወቅት የዜና ዘገባዎችን ይከታተል ስለነበር ሁሉም የቤተሰባችን አባል ከሌላው ሩዋንዳ ውስጥ ካለ ሁሉም ቱትሲ ጋር ወድሟል ብሎ አምኖ ተስፋ ቆርጦ ነበር፡፡ ለመገደል ካልሆነ በቀር በዘር ፍጅቱ ወቅት ወደ ሀገሪቱ የሚመለስበት ምንም መንገድ አልነበረውም፡፡
ለመምጣት ችግር የሆነበት ደግሞ በወቅቱ ለመመለስ ወጪውን መሸፈን አለመቻሉ ነው፡፡ ተማሪ ስለሆነ ገቢ የለውም፣ የሚኖረው 5 000 ኪሎሜትር ርቆ በሴኔጋል ነው፡፡ የአየር መሳፈሪያ ወጭው ብቻ 2 000 የአሜሪካን ዶላር ይፈጃል፤ ይህም የማይታሰብ ነው! ሙሉ ወጭውን ሸፍኖ የሚያስተምረው የአውሮፓ ድርጅትም ሩዋንዳ በጣም አደገኛ የጦርነት ቀጠና ስለሆነ ወደዚያ የምትሄድበትን ክፍያ አልከፍልልህም ይለዋል፡፡ ወንድሜ ትምህርቱን አቋርጦ መጥቶ ከኔ ጋር ለመኖር ቢፈልግም እማማንና አባባን የሚያኮራበት ሁነኛ መንገድ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት መጨረስ እንደሆነ ነገርኩት፡፡ በየሳምንቱ ለመጻጻፍ፣ ለወደፊቱ ለመጠያየቅና ገንዘብም ለማጠራቀም ተስማማን፡፡ እናም አሁን ወደ ማታባ ላገኘሁት የነጻ የአየር ጉዞ ምስጋና ይግባውና ቤታችንን ያለ ብቸኛው ቀሪ ወንድሜ እጎበኛለሁ፡፡
ትንሿ ወታደራዊ ጠያራ መሬት ላይ ካረፈች በኋላ ኮሎኔል ጉዬ ትራኦሬ ለሚባል ብርቱ ወጣት መኰንን አደራ ብለው በወታደሮቹ ምሽግ አስቀምጠውን ይሄዳሉ፡፡ እርሱም ለእያንዳንዱ ወታደር የኮሎኔል ጉዬ ልጆች ናቸው ብሎ አስተዋወቀን፡፡ ከዚህን ጊዜ በፊት በነበሩኝ የወታደር ምሽግ ቆይታዎቼ አግኝቼው የማላውቀውን አገኘሁ - ሳራና እኔ የየራሳችን ክፍል፣ የምንተኛባቸው አልጋዎች፣ ምርጥ ምግብ ብሎም የእያንዳንዱ ወታደር አክብሮትና እገዛ ተቸረን፡፡ እንዲያውም እስከ ንጋት ድረስ ባህላዊ የሴኔጋል ዘፈኖችን ሲዘፍኑና እርስ በርሳቸው ሲቀላለዱ አብረን አነጋን፡፡ ሳራ በአቀባበሉ ደስ ከመሰኘቷም በላይ ደኅንነት ሲሰማት እኔም አገሬ በመግባቴ ደስ ተሰኘሁ፡፡
በማግስቱ ወደ መንደሬ ለመሄድ ስምንት ኪሎሜትር የሚርቀውን የእግር መንገድ ለመጓዝ ስዘገጃጅ መኰንን ትራኦሬ ስለደህንነታችን ያለውን ሥጋት ይናገር ጀመር፡፡ የዘር ፍጅቱ ቢያበቃም በሀገሪቱ ግልጽ የሆነ ጥላቻ ስለነገሰ በዚያን ወቅትም ግድያ ይፈጸማል፡፡ መኰንኑ በትጥቅ አጀብ ሊልከን ወሰነ - አጀቡም ከሁለት ደርዘን ያላነሱ ወታደሮችንና አምስት ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችን ያጠቃልላል፡፡ ማታባ በጀግና ኩራት እንገባለን እንጂ እንደ ተመላሽ ስደተኛ አንሹለከለክም፡፡ በዚያች መንደር ያን ያህል ጊዜ በፍራቻና ሥጋት ተሸሽጌባታለሁ፤ አሁን ግን ራሴን ቀና አድርጌ መሄዴ መልካም ነው፡፡
በልጅነቴ በጣም በማውቀው ሰማይ ስር ተሸከርካሪዎቻችንን ስንነዳ ስሜቴ በፍጥነት ወደ ኃይለኛ ብስጭት ተለወጠ፡፡ ወንድሞቼና እኔ ብዙውን ጊዜ እንሄድበት ወደነበረው መንገድ ስንገባ ማልቀስ ጀመርኩ፤ ከዚያም በወቅቱ ጭር ባለው እናቴ ታስተምርበት በነበረው ትምህርት ቤት አልፈን አባታችንን ተከትለን በጠዋት ኪቩ ሐይቅ ወርደን ልንዋኝ በምናልፍበት መንገድ ቁልቁል ወረድን፡፡ ሳራ እጇን በትከሻዬ አድርጋ ልታጽናናኝ ብትሞክርም አልሆነም - መጽናናት የምችል አልነበርኩም፡፡ በፈራረሱ መስኮቶችና በተዘጉ የውጪ በሮች አጮልቀው የሚያዩን ፊቶች ጥላ ይታየኛል … ብዙ ወገኖቼን አሳደው የገደሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ፊቶች፡፡ ብዙዎቹን የቱትሲዎችን ቤቶች ራሳቸው ካቃጠሉ በኋላ አሁን ብቻቸውን ቆመው ያሉትን ብቸኛ ቤቶች በንብረትነት ይዘዋቸዋል፡፡ ከዚያም የራሴ ቤት ጋ ደረስን፡፡
ጣራ የለ፣ መስኮት የለ፣ በር የለ፤ ሙሉ በሙሉ ወድሟል፡፡ ገዳዮቹ ለጭፍጨፋቸው ሲዘገጃጁ እኛ ለቀናት ሬድዮ ስናዳምጥበት የነበረውን የተቃጠለውን መሬት የተወሰኑ ከፊል ግንቦች እየጠበቁት ዘብ ቆመዋል፡፡ አንድ ወቅት የወላጆቼ ሕልም የነበሩትን ባዶ ክፍሎች እየቃኘሁ በድንጋይ መዋቅሩ ውስጥ ተዟዟርኩ፡፡ የተጎዱ የቤት እቃዎችም ሆኑ የተቃጠሉ ልብሶች አሻራ የለም - ማንም ሊገምት እንደሚችለው ቤቱ ከመጋየቱ በፊት ንብረታችን ተዘርፏል፡፡
ብዙ በሕይወት የተረፉ ቱትሲ ጎረቤቶቻችን ወታደራዊ አጀባችንን አይተው ሰላም ሊሉኝ መጡ፡፡ በተደበቅኩባቸው ጊዜያት ስለተከሰቱት መጥፎ ነገሮች ነገሩኝ፤ እናቴ በተቀበረችበት ቦታ ላይ ሆነንም እምዬ እናቴ አንዴት እንደተገደለች ያስረዱኝ
👍1