#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ሀገር_ቤት
፡
ሁልጊዜ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ የጥላቻ ድምፅ እሰማለሁ፡፡ የአር.ቲ. ኤል. ኤም. ሬድዮ የጥላቻ ድምጾች በመኝታ ቤቴ መስኮት ገብተው ህልሞቼ ውስጥ እስኪደነቀሩ ሌሊቱን በሰላም ተኝቼ አሳልፋለሁ፡፡ ልብ ይበሉ፣ በሦስተኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ አር. ቲ. ኤል. ኤም. በጽንፈኛ ሁቱዎች ዘንድ አዲሱና በጣም ታዋቂው ሬድዮ ጣቢያ ለመሆን ችሏል፡፡ ጸረ-ቱትሲ መርዝን የሚረጭ የተለየ የጥላቻ መሣሪያ ወጥቶታል፡፡
ሁሌ ‹‹ስለ ሁቱ የበላይነት›› የሚጮህ አካል-አልባ ክፉ ድምፅ ሆነ፡፡ የሁቱ የበላይነትም ሁቱዎችን በቱትሲ ወዳጆቻቸውና ጎረቤቶቻቸው ላይ እንዲነሱ የሚያደርግ ተናዳፊ ተርብ ለመሆን ቻለ፡፡ ‹‹እነዚያ በረሮ ቱትሲዎች ሊገድሉን ወጥተዋል፡፡ አትመኗቸው… እኛ ሁቱዎች ቀድመናቸው ልንነሳ ይገባናል! መንግሥታችንን ገልብጠው ሊያሳድዱን እየዶለቱብን ነው፡፡ በርዕሰ-ብሔራችን ላይ አንዳች ነገር ቢከሰት ሁሉንም ቱትሲዎች ወዲያውኑ ማውደም ግድ ይለናል! እያንዳንዱ ሁቱ ሩዋንዳን ከነዚህ ቱትሲ በረሮዎች ለማጽዳት እጅ ለእጅ መያያዝ
አለበት! የሁቱ የበላይነት! የሁቱ የበላይነት!››
ይህን በመሰለ አጉለኛ ሁኔታ ከእንቅልፌ እነቃለሁ፡፡ በእርግጥ ዘገባዎቹ እጅጉን በሚያስጠላ ሁኔታ እንጭጭ በመሆናቸው አልፎ አልፎ ያሥቃሉ፡፡ እነዚያን የልጅ ስድቦችና ልቅ ማስፈራሪያዎች ማንም ሰው ከምር ይቀበላቸዋል ብሎ ማመን አሰቸጋሪ ሲሆን መንግሥቱም የሕዝብ ንብረት የሆነውን የአየር ሰዓት ቱትሲዎችን ለማስፈራሪያ መፍቀዱን ማወቁ ይረብሻል፡፡ በወቅቱ ግን በሀገሪቱ በርካታ ስፍራዎች ቱትሲዎች በጽንፈኞች እየተገደሉ መሆኑን በሚገልጹ ወሬዎች ይበልጡን ተረበሽኩ፡፡ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እንዳሉት ጓደኞቼ ሁሉ በመገናኛ ብዙሃን ስለሚተላለፉት ዘገባዎች ብዙ ላለማሰብና ላለማውራት ሞከርኩ፡፡ ቤተሰቤ ሁሌ አስደሳችና ልዩ ጊዜ የሚያሳልፍበት የትንሣኤ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ ይህን የበዓል ወቅት ጎረቤቶቻችንን በመጋበዝና ወዳጅ-ዘመዶቻችንን በመጠየቅ እቤታችን እናሳልፋለን፡፡ የቤተሰቡ አባላት በሙሉ የምንገናኝበትን የትንሣኤን በዓል እቤቴ ማሳለፍ አምልጦኝ የማያውቅ ቢሆንም እየቀረቡ መጥተው ለነበሩት ፈተናዎቼ ለመዘጋጀት ያግዘኝ ዘንድ በትምህርት ቤቱ ለመቆየት ፈለግሁ፡፡ በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት ቆርጫለሁ፡፡ ወላጆቼ ስልክ ስላልነበራቸው ለአባቴ ለምን እቤት እንደማልሄድ የሚያብራራ ደብዳቤ ጻፍኩለት፡፡ ወላጆቼ ሁልጊዜ ልጆቻቸው የተሻለ ውጤት ያመጡ ዘንድ
ከሚጠበቀው በላይ እንዲያጠኑ ስለሚፈልጉ ቅር እንደማይሰኙብኝ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይህ ለካ ትልቅ ስህተት ኖሯል!
አባቴ እቤት እንድሄድ የሚለምን ደብዳቤ ጻፈልኝ፡፡ እንዲያውም የጠየቀኝ የትምህርት ቤት እረፍቴ እስኪደርስ ሳልጠብቅ ወዲያውኑ እንድሄድ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንድሆን እንደሚፈልግና እቤት ያላንዳች ረብሻ ማጥናት እንደሚቻለኝ ቃል ገባልኝ፡፡ ልባዊ ተማጽኖው በዓይኖቼ እንባ ሞላባቸው፡፡ ውድ ልጄ፣
ትምህርት አንቺን ከኛ እንደነጠቀን ይሰማኛል፡፡ እናትሽና እኔ እረፍትሽ እስኪጀምር በጉጉት እየጠበቅን ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀመረ አንቺ እቤት መጥተሽ እንደገና እንደ ቤተሰብ ስለምንኖር ነው፡፡ መምጣትሽን እንፈልገዋለን፤ ወላጆችሽ ነን፤ እንወድሻለን፤ በእጅጉ እንናፍቅሽማለን - ይህን ሃቅ በፍጹም አትርሺው! ለሁለት ቀናት ቢሆንም እንኳን ልታዪን ልትመጪ ግድ ይልሻል፤ ጊዜውን ለሌላ ለምንም ጉዳይ መስዋዕት እንዳታደርጊው፡፡ ነዪልን፤ አብሮነትሽን እንፈልገዋለን …
ደብዳቤውን አንብቤ ሳልጨርሰው ወደ ቤት ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ ከወላጆቼ ጋር ስድስት ቀናትን አሳልፌ ለፈተናዎቼ በሳምንቱ መጨረሻ ትምህርት ቤት ለመመለስ አቀድኩ፡፡ የጉዞ ዝግጅቴን ሳደርግ የሳራ ታናሽ ወንድም የሆነው ኦገስቲን ከእኔ ጋር ለበዓሉ ወደ ወላጆቼ ቤት ሄዶ መዋል ይችል እንደሆን ጠየቀኝ፡፡ ኦገስቲን የወንድሜ የቪያኒ የልብ ጓደኛ ሲሆን የመንፈቀ-ዓመቱን ትምህርቱን ኪጋሊ ላይ ካገባደደ በኋላ በትምህርት ቤት መኝታ ቤታችን ውስጥ ቆይቷል፡፡ መለሎው፣ መልከ-ቀናውና አስደሳቹ የ18 ዓመቱ ኦገስቲን ከቪያኒ በቀር ማንም ሰው ፊት አያወራም፡፡ እንግዳችን ቢሆንልን እንደምንደሰት ነገርኩት፡፡
ኦገስቲንና እኔ ማታባ ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ደረስን፤ የቤተሰቤም አባላት በመምጣቴ በእጅጉ ተደሰቱ፡፡ በሳይንስ የድህረ-ምረቃ ትምህርቱን ለመከታተል ዓለም አቀፍ የትምህርት ዕድል ካገኘው ከኤይማብል በስተቀር ቤተሰቡ ተሟልቷል፡፡ ኤይማብል አገሪቱን ለቆ ከ5 000 ኪሎሜትሮች በላይ ወደምትርቀው ሴኔጋል ሄዷል፡፡ ዳማሲን በበኩሉ በታሪክ በሁለተኛ ዲግሪ ከተመረቀ ጀምሮ ከሚያስተምርበት ከኪጋሊ ተሳፍሮ መጥቷል፡፡ ቪያኒም ከአዳሪ ትምህርት ቤት ተመልሷል፡፡
የመጀመሪያዋን ቀን ከዳማሲን የመንደር ወሬ ስሰማ፣ ጓደኞቼን ስጠይቅ፣ ከቪያኒ ጋር ስንጫወትና ስንከራከር አሳለፍኩ፡፡ በመጭው ቀን፣ በትንሳኤ እለት፣ አብረን ጥሩ ምግብ በላን፡፡ አምላክን ስለሰጠን ነገር ሁሉ አመስግነን በቤተሰባችንና በመንደራችን ስላለው ስለ ሁሉም ሰው ደህንነት ጸለይን - በተጨማሪም ስለብቸኛው ቀሪ አባላችን ስለ ኤይማብል ልዩ ጸሎት አደረስን፡፡ በላያችን ያንዣብብ ከነበረው የፖለቲካ ውጥረት በስተቀር አዝናኝ ጊዜ በማሳለፍ ላይ ነን፡፡ ከወላጆቼ ጋር በመሆኔ ደህንነትና ችግር-አልባነት ተሰማኝ - ይህም የሆነው ምንም ነገር ቢከሰት ታጽናናን ዘንድ እናቴ ስለምትኖርና አባቴም እኛን የመከላከሉን ሥራ ስለሚሠራ ነው፡፡ ቢያንስ ያንን ነው ያሰብኩት ፡፡
ይህ ምሽት የኛ ዓለም እስከዘላለሙ ልትቀየር ትንሽ የቀራት መሆኑን ለመገመት የሚያዳግትበት እንደወትሮው ያለ ምሽት መሆኑ ነው፡፡ ስለ ትምህርት፣ ሥራና በመንደሩ እየተከሰተ ስላለው ነገር እቤት ቁጭ ብለን እናወራለን፡፡ እናታችን ስለ ሠብሉ ስትነግረን አባታችን ደግሞ የቡና ኅብረት-ሥራው የትምህርት ወጪያቸውን ስለሚሸፍንላቸው ሕፃናት ያወራልናል፡፡ ኦገስቲንና ቪያኒ ይቃለዳሉ፡፡ እኔ በበኩሌ እየተዝናናሁና ሁሉንም ነገር እየታዘብኩ እቤት በመሆኔ ደስተኝነት ተሰምቶኛል፡፡ ያልተደሰተው ዳማሲን ብቻ ነው፡፡ ሁልጊዜ በዓል ላይ ሕይወት የሚዘራው እሱ የነበረ ቢሆንም ምሽቱን ሙሉ ሲብሰለሰልና በሥጋት ሲናጥ ቆይቷል፡፡
‹‹ዳማሲን ምን ሆነሃል?›› ስል ጠየኩት፡፡
ወንድሜ ቀና ሲል ዓይኖቻችን ተገጣጠሙ፡፡ ከዚያም በኋላ ዝም ብሎ መቆየት አልተቻለውም፡፡ በተጣደፈ ቃላትና ስሜት ሸክሙን እኔ ላይ አቃለለ - ‹‹ኢማኪዩሌ አይቻቸዋለሁ፤ ገዳዮቹን አይቻቸዋለሁ፡፡ ወደ ቦን ቤት ስንሄድ በርቀት አይተናቸዋል፡፡ የኢንተርሃምዌን ባለ ደማቅ ቀለማት ልብሶች ለብሰዋል፤ የእጅ ቦምቦችንም ይዘዋል፤
ቦምቦች ነበሯቸው ኢማኪዩሌ!›› ሲል ድምጹ አሰቀቀኝ፡፡
ሁሉም ሰው ንግግሩን ስለሰማው ቤቱ እርጭ አለ፡፡ ወላጆቼ እርስ በርሳቸው ተያዩና ዳማሲንን አዩት፡፡
አባቴ ልጁን ለማረጋጋት ሲል ‹‹ምናልባት ሐሳብህ አሸንፎህ እየወጣ እንዳይሆን›› አለው፡፡ ‹‹ብዙ መጥፎ ወሬ ይሰማል፡፡ ሰዎችም አደጋን በሌለበት እያዩት ነው፡፡››
‹‹አይ፣ ዝም ብዬ እኮ እየቃዠሁ አይደለም›› አለ ዳማሲን በድንገት ቆሞ የጉዳዩን አጣዳፊነት በሚያንጸባርቅ መልኩ በመናገር፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ሀገር_ቤት
፡
ሁልጊዜ ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ የጥላቻ ድምፅ እሰማለሁ፡፡ የአር.ቲ. ኤል. ኤም. ሬድዮ የጥላቻ ድምጾች በመኝታ ቤቴ መስኮት ገብተው ህልሞቼ ውስጥ እስኪደነቀሩ ሌሊቱን በሰላም ተኝቼ አሳልፋለሁ፡፡ ልብ ይበሉ፣ በሦስተኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ አር. ቲ. ኤል. ኤም. በጽንፈኛ ሁቱዎች ዘንድ አዲሱና በጣም ታዋቂው ሬድዮ ጣቢያ ለመሆን ችሏል፡፡ ጸረ-ቱትሲ መርዝን የሚረጭ የተለየ የጥላቻ መሣሪያ ወጥቶታል፡፡
ሁሌ ‹‹ስለ ሁቱ የበላይነት›› የሚጮህ አካል-አልባ ክፉ ድምፅ ሆነ፡፡ የሁቱ የበላይነትም ሁቱዎችን በቱትሲ ወዳጆቻቸውና ጎረቤቶቻቸው ላይ እንዲነሱ የሚያደርግ ተናዳፊ ተርብ ለመሆን ቻለ፡፡ ‹‹እነዚያ በረሮ ቱትሲዎች ሊገድሉን ወጥተዋል፡፡ አትመኗቸው… እኛ ሁቱዎች ቀድመናቸው ልንነሳ ይገባናል! መንግሥታችንን ገልብጠው ሊያሳድዱን እየዶለቱብን ነው፡፡ በርዕሰ-ብሔራችን ላይ አንዳች ነገር ቢከሰት ሁሉንም ቱትሲዎች ወዲያውኑ ማውደም ግድ ይለናል! እያንዳንዱ ሁቱ ሩዋንዳን ከነዚህ ቱትሲ በረሮዎች ለማጽዳት እጅ ለእጅ መያያዝ
አለበት! የሁቱ የበላይነት! የሁቱ የበላይነት!››
ይህን በመሰለ አጉለኛ ሁኔታ ከእንቅልፌ እነቃለሁ፡፡ በእርግጥ ዘገባዎቹ እጅጉን በሚያስጠላ ሁኔታ እንጭጭ በመሆናቸው አልፎ አልፎ ያሥቃሉ፡፡ እነዚያን የልጅ ስድቦችና ልቅ ማስፈራሪያዎች ማንም ሰው ከምር ይቀበላቸዋል ብሎ ማመን አሰቸጋሪ ሲሆን መንግሥቱም የሕዝብ ንብረት የሆነውን የአየር ሰዓት ቱትሲዎችን ለማስፈራሪያ መፍቀዱን ማወቁ ይረብሻል፡፡ በወቅቱ ግን በሀገሪቱ በርካታ ስፍራዎች ቱትሲዎች በጽንፈኞች እየተገደሉ መሆኑን በሚገልጹ ወሬዎች ይበልጡን ተረበሽኩ፡፡ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እንዳሉት ጓደኞቼ ሁሉ በመገናኛ ብዙሃን ስለሚተላለፉት ዘገባዎች ብዙ ላለማሰብና ላለማውራት ሞከርኩ፡፡ ቤተሰቤ ሁሌ አስደሳችና ልዩ ጊዜ የሚያሳልፍበት የትንሣኤ በዓል እየደረሰ ነው፡፡ ይህን የበዓል ወቅት ጎረቤቶቻችንን በመጋበዝና ወዳጅ-ዘመዶቻችንን በመጠየቅ እቤታችን እናሳልፋለን፡፡ የቤተሰቡ አባላት በሙሉ የምንገናኝበትን የትንሣኤን በዓል እቤቴ ማሳለፍ አምልጦኝ የማያውቅ ቢሆንም እየቀረቡ መጥተው ለነበሩት ፈተናዎቼ ለመዘጋጀት ያግዘኝ ዘንድ በትምህርት ቤቱ ለመቆየት ፈለግሁ፡፡ በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት ቆርጫለሁ፡፡ ወላጆቼ ስልክ ስላልነበራቸው ለአባቴ ለምን እቤት እንደማልሄድ የሚያብራራ ደብዳቤ ጻፍኩለት፡፡ ወላጆቼ ሁልጊዜ ልጆቻቸው የተሻለ ውጤት ያመጡ ዘንድ
ከሚጠበቀው በላይ እንዲያጠኑ ስለሚፈልጉ ቅር እንደማይሰኙብኝ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ይህ ለካ ትልቅ ስህተት ኖሯል!
አባቴ እቤት እንድሄድ የሚለምን ደብዳቤ ጻፈልኝ፡፡ እንዲያውም የጠየቀኝ የትምህርት ቤት እረፍቴ እስኪደርስ ሳልጠብቅ ወዲያውኑ እንድሄድ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንድሆን እንደሚፈልግና እቤት ያላንዳች ረብሻ ማጥናት እንደሚቻለኝ ቃል ገባልኝ፡፡ ልባዊ ተማጽኖው በዓይኖቼ እንባ ሞላባቸው፡፡ ውድ ልጄ፣
ትምህርት አንቺን ከኛ እንደነጠቀን ይሰማኛል፡፡ እናትሽና እኔ እረፍትሽ እስኪጀምር በጉጉት እየጠበቅን ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀመረ አንቺ እቤት መጥተሽ እንደገና እንደ ቤተሰብ ስለምንኖር ነው፡፡ መምጣትሽን እንፈልገዋለን፤ ወላጆችሽ ነን፤ እንወድሻለን፤ በእጅጉ እንናፍቅሽማለን - ይህን ሃቅ በፍጹም አትርሺው! ለሁለት ቀናት ቢሆንም እንኳን ልታዪን ልትመጪ ግድ ይልሻል፤ ጊዜውን ለሌላ ለምንም ጉዳይ መስዋዕት እንዳታደርጊው፡፡ ነዪልን፤ አብሮነትሽን እንፈልገዋለን …
ደብዳቤውን አንብቤ ሳልጨርሰው ወደ ቤት ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ ከወላጆቼ ጋር ስድስት ቀናትን አሳልፌ ለፈተናዎቼ በሳምንቱ መጨረሻ ትምህርት ቤት ለመመለስ አቀድኩ፡፡ የጉዞ ዝግጅቴን ሳደርግ የሳራ ታናሽ ወንድም የሆነው ኦገስቲን ከእኔ ጋር ለበዓሉ ወደ ወላጆቼ ቤት ሄዶ መዋል ይችል እንደሆን ጠየቀኝ፡፡ ኦገስቲን የወንድሜ የቪያኒ የልብ ጓደኛ ሲሆን የመንፈቀ-ዓመቱን ትምህርቱን ኪጋሊ ላይ ካገባደደ በኋላ በትምህርት ቤት መኝታ ቤታችን ውስጥ ቆይቷል፡፡ መለሎው፣ መልከ-ቀናውና አስደሳቹ የ18 ዓመቱ ኦገስቲን ከቪያኒ በቀር ማንም ሰው ፊት አያወራም፡፡ እንግዳችን ቢሆንልን እንደምንደሰት ነገርኩት፡፡
ኦገስቲንና እኔ ማታባ ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ደረስን፤ የቤተሰቤም አባላት በመምጣቴ በእጅጉ ተደሰቱ፡፡ በሳይንስ የድህረ-ምረቃ ትምህርቱን ለመከታተል ዓለም አቀፍ የትምህርት ዕድል ካገኘው ከኤይማብል በስተቀር ቤተሰቡ ተሟልቷል፡፡ ኤይማብል አገሪቱን ለቆ ከ5 000 ኪሎሜትሮች በላይ ወደምትርቀው ሴኔጋል ሄዷል፡፡ ዳማሲን በበኩሉ በታሪክ በሁለተኛ ዲግሪ ከተመረቀ ጀምሮ ከሚያስተምርበት ከኪጋሊ ተሳፍሮ መጥቷል፡፡ ቪያኒም ከአዳሪ ትምህርት ቤት ተመልሷል፡፡
የመጀመሪያዋን ቀን ከዳማሲን የመንደር ወሬ ስሰማ፣ ጓደኞቼን ስጠይቅ፣ ከቪያኒ ጋር ስንጫወትና ስንከራከር አሳለፍኩ፡፡ በመጭው ቀን፣ በትንሳኤ እለት፣ አብረን ጥሩ ምግብ በላን፡፡ አምላክን ስለሰጠን ነገር ሁሉ አመስግነን በቤተሰባችንና በመንደራችን ስላለው ስለ ሁሉም ሰው ደህንነት ጸለይን - በተጨማሪም ስለብቸኛው ቀሪ አባላችን ስለ ኤይማብል ልዩ ጸሎት አደረስን፡፡ በላያችን ያንዣብብ ከነበረው የፖለቲካ ውጥረት በስተቀር አዝናኝ ጊዜ በማሳለፍ ላይ ነን፡፡ ከወላጆቼ ጋር በመሆኔ ደህንነትና ችግር-አልባነት ተሰማኝ - ይህም የሆነው ምንም ነገር ቢከሰት ታጽናናን ዘንድ እናቴ ስለምትኖርና አባቴም እኛን የመከላከሉን ሥራ ስለሚሠራ ነው፡፡ ቢያንስ ያንን ነው ያሰብኩት ፡፡
ይህ ምሽት የኛ ዓለም እስከዘላለሙ ልትቀየር ትንሽ የቀራት መሆኑን ለመገመት የሚያዳግትበት እንደወትሮው ያለ ምሽት መሆኑ ነው፡፡ ስለ ትምህርት፣ ሥራና በመንደሩ እየተከሰተ ስላለው ነገር እቤት ቁጭ ብለን እናወራለን፡፡ እናታችን ስለ ሠብሉ ስትነግረን አባታችን ደግሞ የቡና ኅብረት-ሥራው የትምህርት ወጪያቸውን ስለሚሸፍንላቸው ሕፃናት ያወራልናል፡፡ ኦገስቲንና ቪያኒ ይቃለዳሉ፡፡ እኔ በበኩሌ እየተዝናናሁና ሁሉንም ነገር እየታዘብኩ እቤት በመሆኔ ደስተኝነት ተሰምቶኛል፡፡ ያልተደሰተው ዳማሲን ብቻ ነው፡፡ ሁልጊዜ በዓል ላይ ሕይወት የሚዘራው እሱ የነበረ ቢሆንም ምሽቱን ሙሉ ሲብሰለሰልና በሥጋት ሲናጥ ቆይቷል፡፡
‹‹ዳማሲን ምን ሆነሃል?›› ስል ጠየኩት፡፡
ወንድሜ ቀና ሲል ዓይኖቻችን ተገጣጠሙ፡፡ ከዚያም በኋላ ዝም ብሎ መቆየት አልተቻለውም፡፡ በተጣደፈ ቃላትና ስሜት ሸክሙን እኔ ላይ አቃለለ - ‹‹ኢማኪዩሌ አይቻቸዋለሁ፤ ገዳዮቹን አይቻቸዋለሁ፡፡ ወደ ቦን ቤት ስንሄድ በርቀት አይተናቸዋል፡፡ የኢንተርሃምዌን ባለ ደማቅ ቀለማት ልብሶች ለብሰዋል፤ የእጅ ቦምቦችንም ይዘዋል፤
ቦምቦች ነበሯቸው ኢማኪዩሌ!›› ሲል ድምጹ አሰቀቀኝ፡፡
ሁሉም ሰው ንግግሩን ስለሰማው ቤቱ እርጭ አለ፡፡ ወላጆቼ እርስ በርሳቸው ተያዩና ዳማሲንን አዩት፡፡
አባቴ ልጁን ለማረጋጋት ሲል ‹‹ምናልባት ሐሳብህ አሸንፎህ እየወጣ እንዳይሆን›› አለው፡፡ ‹‹ብዙ መጥፎ ወሬ ይሰማል፡፡ ሰዎችም አደጋን በሌለበት እያዩት ነው፡፡››
‹‹አይ፣ ዝም ብዬ እኮ እየቃዠሁ አይደለም›› አለ ዳማሲን በድንገት ቆሞ የጉዳዩን አጣዳፊነት በሚያንጸባርቅ መልኩ በመናገር፡
👍2😁1