#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ዩኒቨርሲቲ
፡
በ1991 ክረምት መጨረሻ የማይቻለው ተከሰተ - በቡታሬ በሚገኘው ብሄራዊው ዩኒቨርሲቲ መማር የሚያስችለኝ የትምህርት ዕድል ተሰጠኝ፡፡ በሕይወቴ ሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትን በጽኑ ስመኝ ነበር፡፡ በመሆኑም በፊቴ እነዚያ ሁሉ መሰናክሎች ቢጋረጡብኝም በድንገት ሕልሜ እውን ሆነ፡፡
ወላጆቼ ዜናውን ሲሰሙ በጣም ተደስተው ተቁነጠነጡ፡፡ በትክክለኛው የሩዋንዳ ደንብ - ያው በድግስ መሆኑ ነው - እናከብረው ዘንድም ምግብና መጠጥ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ይሉ ጀመር፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከቤታችን የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ነሽ፣ ስለሆነም አሁኑኑ ይህን ለሁሉም ሰው ማሳወቅ አለብን!›› ሲል አባቴ በኩራት ተናገረ፡፡ በማግስቱ ረጅም መንገድ ተጉዤ ለአያቴ፣ ለአክስቶቼ፣ ለአጎቶቼና ለሁሉም በአቅራቢያችን መንደሮች ለሚኖሩት ልጆቻቸው ወሬውን እንዳበስር አመቻቸልኝ፡፡
ሌሊቱን ሙሉ ስንስቅ፣ ስንበላና ወደፊት ስለሚኖሩት በጎ ነገሮች ሁሉ ስናወጋ አሳለፍን፡፡ ወላጆቼ በዚያ ምሽት ሸክም ከትከሻዎቸው እንደወረደላቸው ሁሉ ወደ ወጣትነት የተመለሱ መሰሉኝ፡፡
እናቴ በደስታ ፈክታ አመሸች፡፡ ‹‹ሁሉም ነገር ላንቺ ብሩህ የሆነልሽ ይመስላል፣ ኢማኪዩሌ›› አለችኝ፡፡ ‹‹ከአሁን በኋላ ሙሉ በሙሉ የራስሽን መንገድ ማበጀት ትችያለሽ፤ ቀና በይ፤ ማንም ሌላ ሰው በገበታሽ ላይ በፍጹም ምግብ እንዲያስቀምጥልሽ አትጠባበቂ፡፡››
አባቴም ከኔ ጋር መጠጫ አጋጭቶ ብዙ አባታዊ ምክር ለገሰኝ፡፡ ‹‹ብዙውን ጊዜ በዩኒቨርሲቲ የሚማሩት ወንዶች ሲሆኑ እነርሱም አንቺን እንደነርሱ ጎበዝ ነች ብለው አያስቡም፡፡ ግን እንደነሱ መትጋት እንደምትችዪ አውቃለሁ፤ አንዲያውም ከማንኛውም ወንድ በተሻለ፡፡ አንቺ ቱትሲ ስለሆንሽ ዩኒቨርሲቲ መግባት ፈተና ሆኖብሽ ቆይቷል፤ ይኸው አስቸጋሪው ወቅት አለፈ፡፡ እንግዲህ የራስሽ ድርሻ ነው - በደንብ አጥኚ፣ ጸልዪ፤ ስታድጊ በስስት እናይሽ እንደነበርሽው ምስጉን፣ ደግና ቆንጆ ልጅ መሆንሽን ቀጥዪበት፡፡››
በጣፋጭና ፍቅር የተሞላባቸው ቃላቱ ልቤ ሐሴት አደረገች፡፡ ‹‹ሃሳብ አይግባህ አባባ›› አልኩት፡፡ ‹‹አንተንም ሆነ እማማን አላሳፍራችሁም፡፡ አኮራችኋለሁ፡፡››
ስለ ሰው ልቦናና አእምሮ አሠራር ለመማር ሥነ ልቦናንና ፍልስፍናን ለማጥናት ብፈልግም የትምህርት ዕድሉ በተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች ባሉ ክፍት ቦታዎች የተወሰነ ስለነበር ራሴ የምፈልገውን የጥናት መስክ እንድመርጥ አልተፈቀደልኝም፡፡ በተግባራዊ ሳይንስ መርሃ-ግብር መመደቤ ተስማምቶኛል፡፡ በሊሴ ለወንድሞቼ ችሎታዬን ለማሳየት ስል ራሴን በሒሳብና ፊዚክስ አብቅቼ ስለነበር አሁን ያ ሥንቅ ይሆነኛል፡፡ ሻንጣዎቼን አዘገጃጅቼ ወዲያውኑ ከመንደሬ ደቡብ ምሥራቅ አራት ሰዓት ወደሚያስነዳውና ፍጹም አዲስ ሕይወት ወደሚጠብቀኝ ወደ ቡታሬ አቀናሁ፡፡
ትምህርት ቤቱ ቅጥር-ግቢ ስደርስ ክሌሜንታይንን ጨምሮ ከሊሴ ስድስቱ የሴት ጓደኞቼ፣ የትምህርት ዕድሉን ማግኘታቸውን ተረዳሁ፡፡ ጓደኛዬ ሳራ እዚያው አንድ ዓመት ቀድማ ገብታ ስትማር የቆየች ሲሆን አንድ መኝታ ክፍል ውስጥ አብረን እንድንኖር ስትጠብቀኝ ኖሯል፡፡ በተጨናነቁ ክፍሎች ውስጥ ከተኛሁባቸው ከእነዚያ ዓመታት በኋላ ከአንዲት ሴት ልጅ ጋር ብቻ አንድ ክፍል መጋራት እጅግ ይመቻል፡፡ ክሌሜንታይን ብዙ ጊዜ የኛን ክፍል ትጎበኝ የነበረ ሲሆን በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን ራሳችንን በኤሌክትሪክ የማቃጠሉን ዕቅዳችንን ባለመፈጸማችን እንዴት ዕድለኞች እንደነበርን በጨዋታ መካከል እናነሳለን፡፡ ያ ቢሆን ኖሮ የዩኒቨርሲቲን አስደሳች ነገሮች ሁሉ መች እናይ ነበር?
ትምህርቱን ወደድኩት፤ በጣም ጠንክሬም አጠና ጀመር፡፡ የዩኒቨርሲቲን አስደሳችነትና ነጻነት እንዴት እንደወደድኩት! የትምህርት ዕድሉ ለእኔ ትልቅ ነገር የነበረውን ወደ 30 የአሜሪካን ዶላር የሚሆን ወርሃዊ የኪስ ገንዘብንም ይጨምራል፡፡ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ትልቅ ሰው ነጻነት ተሰማኝ፡፡ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ መልበስ ቀረልኝ፤ ከተማም ሄድ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር ቆንጆ ቆንጆ ልብሶችን መግዛት ቻልኩ፡፡ አቤት ሲያስደስት!
ቡና ተፈልቶ በሚሸጥባቸው ስፍራዎች፣ በሰንበት ተንቀሳቃሽ ምስል በሚታይባቸው ቦታዎችና በየአሥራ አምስት ቀኑ ቅዳሜ ምሽት በሚካሄዱት የትምህርት ቤት አቀፍ የዳንኪራ ጊዜያት እስከመገኘት ደርሼ በማኅበራዊ ሕይወት በጣም ንቁ ተሳታፊ ሆንኩ፡፡ የትዕይንት ማሳያ ቡድንንም ተቀላቅዬ ብዙውን ጊዜ የቡታሬ ከንቲባ በሚገኙባቸው በሁሉም ትዕይንቶች እዘፍንና እጨፍር ነበር፡፡ ሃይማኖታዊ ገጸባህርያትን ወክሎ መተወን ምርጫዬ በመሆኑ እንዲያውም አንድ ጊዜ የምወዳትን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወክዬ ተጫውቻለሁ፡፡ ሁልጊዜ ለጸሎት የሚሆን ጊዜ እተዋለሁ፡፡ ያንን ጽናት ማግኘቴና ጸሎት ማድረጌ እጅጉን አረጋግቶኝና አትኩሮቴን እንድሰበስብ ረድቶኝ ነበር፡፡ ቤተ-ክርስቲያን በሳምንት ብዙ ጊዜ እሄዳለሁ፤ ከሴት ጓደኞቼም ጋር የጸሎት ቡድን አቋቁሜያለሁ፡፡
ለናፍቆት ጊዜ ባይኖረኝም ከአባቴ የሚላኩልኝ ብቸኝነት የሚንጸባረቅባቸው ደብዳቤዎች ቤተሰቤን ቶሎ ቶሎ መጎብኘት እንዳለብኝ አስገነዘቡኝ፡፡ በወቅቱ ቪያኒ በአዳሪ ትምህርት ቤት ስለነበር ወላጆቼ ብቸኝነትን መላመድ አቅቷቸዋል፡፡ ‹‹ከልጆቼ አንዳቸውም እዚህ ሳይኖሩ ሕይወቴ እንደ ዱሮው ሊሆን አይችልም›› ሲል አባቴ ጻፈልኝ፡፡ ‹‹ቤቱ በጣም ጭር ብሏል፡፡ አንዳንዴ እኔና እናትሽ እርስ በርሳችን እንተያይና እንገረማለን፣ ‹ያ ሁሉ ሣቅ የት ሄደ?› እንላለን፡፡ የራስሽ ልጆች ሲኖሩሽ፣ ኢማኪዩሌ፣ ሳትጠግቢያቸው ስለሚሄዱብሽ አብረውሽ እያሉ እያንዳንዷን ደቂቃ በደስታ ማሳለፍሽን እርግጠኛ ሁኚ፣ …››
በማታባ ያሉትን የተወሰኑትን ጓደኞቼን የሚያውቅ ዮሃንስ የሚባል ተማሪ ጓደኛም አገኘሁ፡፡ ከእኔ ሦስት ዓመት ይበልጥ የነበረና ‹‹ድንገት›› ከኔ ጋር በትምህርት ቤቱ የተለያዩ ስፍራዎች ግጥምጥም የማለት የተለየ ጸባይ የነበረው ልጅ ነው፡፡ መጽሐፍቴን ይይዝልኝ፣ የትምህርት ቤታችንን ግቢ ያሳየኝና ከጓደኞቹ ጋር ያስተዋውቀኝ ጀመር፡፡ አማላይ፣ ታጋሽና ለሰው አሳቢ ልጅ ነበር፡፡ በጫካው ውስጥ ለረጅም የእግር ጉዞ አብረን እየሄድን ለእኛ አስፈላጊ ስለሆነው ጉዳይ እናወራለን - ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ ቤተሰብና ስለ ጥሩ ትምህርት፡፡ በኋላም ላይ ፍቅር ለመጀመር በቃን፤ በመጭዎቹም ዓመታት ውስጥ አንዳችን ለሌላችን በጣም እንተሳሰብ ጀመር፡፡ ዮሃንስ ሁቱ ቢሆንም ግን ይህ ጭራሽ ጉዳያችን አልነበረም፡፡ ለአባቴ ይልቁን ዮሃንስ ወንጌላዊ ክርስቲያንና የሰባኪ ልጅ መሆኑ ያሳስበዋል፡፡
‹‹ካቶሊክ መሆንሽን አትርሺ›› እያለ አባቴ ያስታውሰኛል፡፡ ‹‹ዮሃንስ ጥሩ ልጅ ይመስላል፤ እንድታፈቅሪውም መርቄሻለሁ - ግን ወደ እርሱ ኃይማኖት ሊቀይርሽ እስካልሞከረ ድረስ ነው፡፡›› አባቴ በጣም ታጋሽ ሰው ሲሆን ሃይማኖተኛም ነው በዩኒቨርሲቲ የቆየሁባቸው ሁለቱ የመጀመሪያ ዓመታት በረሩ፤ ሁሉም ነገር መልካም ሆነልኝ - ውጤቴ ጥሩ፣ ቤተሰቤ ጤነኛ፣ ሕይወቴም አስደሳች ሕይወት ስለሚመች አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ጦርነት መኖሩን ለመርሳት አይከብደንም፡፡ አልፎ አልፎ የሚካሄዱ የሰላም ድርድሮችና የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢኖሩም በቱትሲ አማጽያንና በመንግሥት
፡
፡
#ምዕራፍ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_ዩኒቨርሲቲ
፡
በ1991 ክረምት መጨረሻ የማይቻለው ተከሰተ - በቡታሬ በሚገኘው ብሄራዊው ዩኒቨርሲቲ መማር የሚያስችለኝ የትምህርት ዕድል ተሰጠኝ፡፡ በሕይወቴ ሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትን በጽኑ ስመኝ ነበር፡፡ በመሆኑም በፊቴ እነዚያ ሁሉ መሰናክሎች ቢጋረጡብኝም በድንገት ሕልሜ እውን ሆነ፡፡
ወላጆቼ ዜናውን ሲሰሙ በጣም ተደስተው ተቁነጠነጡ፡፡ በትክክለኛው የሩዋንዳ ደንብ - ያው በድግስ መሆኑ ነው - እናከብረው ዘንድም ምግብና መጠጥ ለማዘጋጀት ተፍ ተፍ ይሉ ጀመር፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ በመግባት ከቤታችን የመጀመሪያዋ ሴት ልጅ ነሽ፣ ስለሆነም አሁኑኑ ይህን ለሁሉም ሰው ማሳወቅ አለብን!›› ሲል አባቴ በኩራት ተናገረ፡፡ በማግስቱ ረጅም መንገድ ተጉዤ ለአያቴ፣ ለአክስቶቼ፣ ለአጎቶቼና ለሁሉም በአቅራቢያችን መንደሮች ለሚኖሩት ልጆቻቸው ወሬውን እንዳበስር አመቻቸልኝ፡፡
ሌሊቱን ሙሉ ስንስቅ፣ ስንበላና ወደፊት ስለሚኖሩት በጎ ነገሮች ሁሉ ስናወጋ አሳለፍን፡፡ ወላጆቼ በዚያ ምሽት ሸክም ከትከሻዎቸው እንደወረደላቸው ሁሉ ወደ ወጣትነት የተመለሱ መሰሉኝ፡፡
እናቴ በደስታ ፈክታ አመሸች፡፡ ‹‹ሁሉም ነገር ላንቺ ብሩህ የሆነልሽ ይመስላል፣ ኢማኪዩሌ›› አለችኝ፡፡ ‹‹ከአሁን በኋላ ሙሉ በሙሉ የራስሽን መንገድ ማበጀት ትችያለሽ፤ ቀና በይ፤ ማንም ሌላ ሰው በገበታሽ ላይ በፍጹም ምግብ እንዲያስቀምጥልሽ አትጠባበቂ፡፡››
አባቴም ከኔ ጋር መጠጫ አጋጭቶ ብዙ አባታዊ ምክር ለገሰኝ፡፡ ‹‹ብዙውን ጊዜ በዩኒቨርሲቲ የሚማሩት ወንዶች ሲሆኑ እነርሱም አንቺን እንደነርሱ ጎበዝ ነች ብለው አያስቡም፡፡ ግን እንደነሱ መትጋት እንደምትችዪ አውቃለሁ፤ አንዲያውም ከማንኛውም ወንድ በተሻለ፡፡ አንቺ ቱትሲ ስለሆንሽ ዩኒቨርሲቲ መግባት ፈተና ሆኖብሽ ቆይቷል፤ ይኸው አስቸጋሪው ወቅት አለፈ፡፡ እንግዲህ የራስሽ ድርሻ ነው - በደንብ አጥኚ፣ ጸልዪ፤ ስታድጊ በስስት እናይሽ እንደነበርሽው ምስጉን፣ ደግና ቆንጆ ልጅ መሆንሽን ቀጥዪበት፡፡››
በጣፋጭና ፍቅር የተሞላባቸው ቃላቱ ልቤ ሐሴት አደረገች፡፡ ‹‹ሃሳብ አይግባህ አባባ›› አልኩት፡፡ ‹‹አንተንም ሆነ እማማን አላሳፍራችሁም፡፡ አኮራችኋለሁ፡፡››
ስለ ሰው ልቦናና አእምሮ አሠራር ለመማር ሥነ ልቦናንና ፍልስፍናን ለማጥናት ብፈልግም የትምህርት ዕድሉ በተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች ባሉ ክፍት ቦታዎች የተወሰነ ስለነበር ራሴ የምፈልገውን የጥናት መስክ እንድመርጥ አልተፈቀደልኝም፡፡ በተግባራዊ ሳይንስ መርሃ-ግብር መመደቤ ተስማምቶኛል፡፡ በሊሴ ለወንድሞቼ ችሎታዬን ለማሳየት ስል ራሴን በሒሳብና ፊዚክስ አብቅቼ ስለነበር አሁን ያ ሥንቅ ይሆነኛል፡፡ ሻንጣዎቼን አዘገጃጅቼ ወዲያውኑ ከመንደሬ ደቡብ ምሥራቅ አራት ሰዓት ወደሚያስነዳውና ፍጹም አዲስ ሕይወት ወደሚጠብቀኝ ወደ ቡታሬ አቀናሁ፡፡
ትምህርት ቤቱ ቅጥር-ግቢ ስደርስ ክሌሜንታይንን ጨምሮ ከሊሴ ስድስቱ የሴት ጓደኞቼ፣ የትምህርት ዕድሉን ማግኘታቸውን ተረዳሁ፡፡ ጓደኛዬ ሳራ እዚያው አንድ ዓመት ቀድማ ገብታ ስትማር የቆየች ሲሆን አንድ መኝታ ክፍል ውስጥ አብረን እንድንኖር ስትጠብቀኝ ኖሯል፡፡ በተጨናነቁ ክፍሎች ውስጥ ከተኛሁባቸው ከእነዚያ ዓመታት በኋላ ከአንዲት ሴት ልጅ ጋር ብቻ አንድ ክፍል መጋራት እጅግ ይመቻል፡፡ ክሌሜንታይን ብዙ ጊዜ የኛን ክፍል ትጎበኝ የነበረ ሲሆን በጦርነቱ መጀመሪያ ሰሞን ራሳችንን በኤሌክትሪክ የማቃጠሉን ዕቅዳችንን ባለመፈጸማችን እንዴት ዕድለኞች እንደነበርን በጨዋታ መካከል እናነሳለን፡፡ ያ ቢሆን ኖሮ የዩኒቨርሲቲን አስደሳች ነገሮች ሁሉ መች እናይ ነበር?
ትምህርቱን ወደድኩት፤ በጣም ጠንክሬም አጠና ጀመር፡፡ የዩኒቨርሲቲን አስደሳችነትና ነጻነት እንዴት እንደወደድኩት! የትምህርት ዕድሉ ለእኔ ትልቅ ነገር የነበረውን ወደ 30 የአሜሪካን ዶላር የሚሆን ወርሃዊ የኪስ ገንዘብንም ይጨምራል፡፡ በሕይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ትልቅ ሰው ነጻነት ተሰማኝ፡፡ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ መልበስ ቀረልኝ፤ ከተማም ሄድ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር ቆንጆ ቆንጆ ልብሶችን መግዛት ቻልኩ፡፡ አቤት ሲያስደስት!
ቡና ተፈልቶ በሚሸጥባቸው ስፍራዎች፣ በሰንበት ተንቀሳቃሽ ምስል በሚታይባቸው ቦታዎችና በየአሥራ አምስት ቀኑ ቅዳሜ ምሽት በሚካሄዱት የትምህርት ቤት አቀፍ የዳንኪራ ጊዜያት እስከመገኘት ደርሼ በማኅበራዊ ሕይወት በጣም ንቁ ተሳታፊ ሆንኩ፡፡ የትዕይንት ማሳያ ቡድንንም ተቀላቅዬ ብዙውን ጊዜ የቡታሬ ከንቲባ በሚገኙባቸው በሁሉም ትዕይንቶች እዘፍንና እጨፍር ነበር፡፡ ሃይማኖታዊ ገጸባህርያትን ወክሎ መተወን ምርጫዬ በመሆኑ እንዲያውም አንድ ጊዜ የምወዳትን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወክዬ ተጫውቻለሁ፡፡ ሁልጊዜ ለጸሎት የሚሆን ጊዜ እተዋለሁ፡፡ ያንን ጽናት ማግኘቴና ጸሎት ማድረጌ እጅጉን አረጋግቶኝና አትኩሮቴን እንድሰበስብ ረድቶኝ ነበር፡፡ ቤተ-ክርስቲያን በሳምንት ብዙ ጊዜ እሄዳለሁ፤ ከሴት ጓደኞቼም ጋር የጸሎት ቡድን አቋቁሜያለሁ፡፡
ለናፍቆት ጊዜ ባይኖረኝም ከአባቴ የሚላኩልኝ ብቸኝነት የሚንጸባረቅባቸው ደብዳቤዎች ቤተሰቤን ቶሎ ቶሎ መጎብኘት እንዳለብኝ አስገነዘቡኝ፡፡ በወቅቱ ቪያኒ በአዳሪ ትምህርት ቤት ስለነበር ወላጆቼ ብቸኝነትን መላመድ አቅቷቸዋል፡፡ ‹‹ከልጆቼ አንዳቸውም እዚህ ሳይኖሩ ሕይወቴ እንደ ዱሮው ሊሆን አይችልም›› ሲል አባቴ ጻፈልኝ፡፡ ‹‹ቤቱ በጣም ጭር ብሏል፡፡ አንዳንዴ እኔና እናትሽ እርስ በርሳችን እንተያይና እንገረማለን፣ ‹ያ ሁሉ ሣቅ የት ሄደ?› እንላለን፡፡ የራስሽ ልጆች ሲኖሩሽ፣ ኢማኪዩሌ፣ ሳትጠግቢያቸው ስለሚሄዱብሽ አብረውሽ እያሉ እያንዳንዷን ደቂቃ በደስታ ማሳለፍሽን እርግጠኛ ሁኚ፣ …››
በማታባ ያሉትን የተወሰኑትን ጓደኞቼን የሚያውቅ ዮሃንስ የሚባል ተማሪ ጓደኛም አገኘሁ፡፡ ከእኔ ሦስት ዓመት ይበልጥ የነበረና ‹‹ድንገት›› ከኔ ጋር በትምህርት ቤቱ የተለያዩ ስፍራዎች ግጥምጥም የማለት የተለየ ጸባይ የነበረው ልጅ ነው፡፡ መጽሐፍቴን ይይዝልኝ፣ የትምህርት ቤታችንን ግቢ ያሳየኝና ከጓደኞቹ ጋር ያስተዋውቀኝ ጀመር፡፡ አማላይ፣ ታጋሽና ለሰው አሳቢ ልጅ ነበር፡፡ በጫካው ውስጥ ለረጅም የእግር ጉዞ አብረን እየሄድን ለእኛ አስፈላጊ ስለሆነው ጉዳይ እናወራለን - ስለ እግዚአብሔር፣ ስለ ቤተሰብና ስለ ጥሩ ትምህርት፡፡ በኋላም ላይ ፍቅር ለመጀመር በቃን፤ በመጭዎቹም ዓመታት ውስጥ አንዳችን ለሌላችን በጣም እንተሳሰብ ጀመር፡፡ ዮሃንስ ሁቱ ቢሆንም ግን ይህ ጭራሽ ጉዳያችን አልነበረም፡፡ ለአባቴ ይልቁን ዮሃንስ ወንጌላዊ ክርስቲያንና የሰባኪ ልጅ መሆኑ ያሳስበዋል፡፡
‹‹ካቶሊክ መሆንሽን አትርሺ›› እያለ አባቴ ያስታውሰኛል፡፡ ‹‹ዮሃንስ ጥሩ ልጅ ይመስላል፤ እንድታፈቅሪውም መርቄሻለሁ - ግን ወደ እርሱ ኃይማኖት ሊቀይርሽ እስካልሞከረ ድረስ ነው፡፡›› አባቴ በጣም ታጋሽ ሰው ሲሆን ሃይማኖተኛም ነው በዩኒቨርሲቲ የቆየሁባቸው ሁለቱ የመጀመሪያ ዓመታት በረሩ፤ ሁሉም ነገር መልካም ሆነልኝ - ውጤቴ ጥሩ፣ ቤተሰቤ ጤነኛ፣ ሕይወቴም አስደሳች ሕይወት ስለሚመች አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ጦርነት መኖሩን ለመርሳት አይከብደንም፡፡ አልፎ አልፎ የሚካሄዱ የሰላም ድርድሮችና የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢኖሩም በቱትሲ አማጽያንና በመንግሥት
👍1