#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....“ጉድ! ጉድ!” አለ፣ ወይዘሮ ጌጤነሽ ሳይቀደሙ ለመቅደም። ቆመው እጅና እግራቸውን በእርጥብ እጃቸው ያባብሳሉ።
ባላምባራስ ዝም አሉ።
ወይዘሮ ጌጤነሽ ባላቸው፣ “ምንድርነው?” ሳይሏቸው በመቅረታቸው ቅር ተሰኙ። ወሬውን ለማውራት የነበራቸውን ጉጉት ስለአመከኑባቸው
ወሽመጣቸው ተቆረጠ። የባላቸውን ዝምታ አሰቡና ነገሩ ከነከናቸው።.
“ምንድርነውም አይሉ?” አሏቸው፣ የጎሪጥ እያይዋቸው።
“የትም አምሽተሽ መተሽ ደሞ ጉድ ትያለሽ?” አሉ፣ ባላምባራስ።
“ነገረኛ፣ ታሞ አይተኛ አሉ” አሉ፣ ወይዘሮ ጌጤነሽ፣ ድምፃቸውን
ዝቅ አድርገው።
“ምን አልሽ?”
“ምን እላለሁ ሳናግርዎ መልስ አይሰጡም ወይ ነው ያልሁት። ሌላ ምን እላለሁ?” አሉ፣ ራት ለመሥራት ምድጃ ላይ ድስት የጣደችውን የቤት አገልጋይ እያዩ።
“ሚሰማሽ ካገኘሽ ምላስሽ ረዥም ነው።”
“ኸርሶ አይበልጥ” አሉ፣ አሁንም ቀስ ብለው።
ባላምባራስ ቆጣ ብለው፣ “ምን አልሽ?” ካሉ በኋላ፣ ጉድ ከሰሙ
ስለ ሰነበቱ ጉዱን የመስማት ፍላጎት አደረባቸው። ቁጣቸውን ገታ አድርገው፣ “እና ምንድርነው ጉዱ?” አሉ፣ ለጠጥ ብለው እምብዛም ለወሬ የጓጉ እንዳይመስሉ።
ወይዘሮ ጌጤነሽ እንዳልሰማ ዝም አሉ፤ እንደ ማኩረፍ አድርጓቸዋል።
“ምንድርነው ጉዱ አልሁሽ እኮ” አሉ ባላምባራስ፣ ቆጣ ብለው።
ወይዘሮ ጌጤነሽ አሁንም ያልሰሙ መሰሉ።
“ሳናግርሽ መልስ 'ማሰጪ?” የባላምባራስ ቁጣ እየተጋጋለ ነው።
“ምን አሉኝ?” አሉ ወይዘሮ ጌጤነሽ። ፊታቸው ላይ ስስ ፈገግታ ይነበባል። ዛሬ አነስተኛ ቢሆንም ባላቸው ላይ ድል ተቀዳጅተዋል።
እነዚህን መሳይ ጥቃቅን ድሎች ናቸው አንዳንዴ ባላቸውን ያሸነፉ
እንዲመስላቸው የሚያደርጓቸው።
“ጉድ እያልሽ ገባሽ። ምንድርነው ብልሽ አለመጥሽ።” አሁንም
ድምፃቸው ገኗል፣ ባላምባራስ ሁነኝ።
“አልሰማሁ ሁኜ ነው” አሉ፣ ወይዘሮ ጌጤነሽ። የባላቸው ቁጣ
የሚገነፍልበትን አፍታ ስለሚያውቁ ያገኙትን ድል እያጣጣሙ፣
“የግራማች ልዥ ...” ሲሉ ጀመሩ።
“ግራማች?” ሲሉ አቋረጧቸው፣ ባላምባራስ። ወሬውን ለመስማት
ቸኩለዋል።
“ግራማች መንበር ናቸዋ።”
“ኸሷው ጋር ስታወሪ እንደቆየሽ አውቄያለሁ። ወልደልዑል ምንን
ሆነ?”
“ሴቷ ወለቴ።”
ጥላዬ፣ የሆነ ነገር እንዳለ ደመነፍሱ ነገረው። ነፍሱ ከዳችው። ጉዱን ለመስማት ቤት ውስጥ መግባት ፈልጎ፣ ወገቡ አልታዘዝ፣ ጉልበቱ አልንቀሳቀስ አለው። እንደምንም ብሎ ተነስቶ ውስጥ ገብቶ መደብ
ላይ ተቀመጠ።
ባላምባራስ በመገረም ተመለከቱት። እሳቸው ሳይተኙ ቤት ውስጥ ስለማይገባ፣ ዐይኑን ካዩት ከርመዋል። ሆዳቸው ተገላበጠ።
“እና ምንን ሆነች?” አሉ፣ መባባታቸው እንዳይታወቅባቸው
እየታገሉ።
ወይዘሮ ጌጤነሽ ከመናገር ተቆጠቡ። ጥላዬን ሰረቅ አድረገው አዩት።እሱ የሚሉትን ለመስማት ቢጓጓም ጎንበስ ብሎ መሬቱን በስንጥር መጫጫር ጀመረ።
“ዛሬ ምንን ነክቶሻል? ምንን ሆነች ስልሽ መልስ ማሰጪ?”
“በያ ሰሞን ንዳድ ይዟቸው ኸነሱ ዘንድ ተኝተው የነበሩት ለካስ
ንጉሡ ኑረዋል...”
“ንጉሠ?”
“አዎ።”
“አጤ በካፋ?”
“እሳቸው። ሌላ ንጉሥ አለ?”
“ምንድርነው ምታወሪው?” አሉ ባላምባራስ፣ የሚስታቸውን ትንኮሳ
ችላ ብለው።
መንን
“አጤ በካፋ ራሳቸው። ወለቴ አስታማቸው ስታበቃ ዛሬ ሰዎች
ኸጥሎሽ ጋር ሰደዱ።”
“ሊያገቧት?”
“ኋላ?”
ጥላዬ ዱብ ዕዳ ሆነበት፣ ድንጋጤ ሰውነቱን አብረከረከው። ተነስቶ
ሊወጣ ፈልጎ ወሬ ለመስማት ተቀመጠ።
“ሰው ለማንጓጠጥ ማን ብሎሽ። ወረኛ! ደሞ ማታመጪው የለ” አሉ
ባላምባራስ፣ ተደናግጠዋል፣ ንዴትም ተናንቋቸዋል።
“እንዴት በሉ? ምን ያልሆነ አምጥቸ አውቃለሁ? ኸመሽ አገር ሁሉ ሚያወራው እኼንኑ ማዶል? የጣ ፈንታ ነገር ይገርማል።”
“ውነት ነው፤ ዕጣ ፈንታ ነው” አለ ጥላዬ፣ የሞት ሞቱን። ሰውነቱ
እየራደ ነው። ለራሱ፣ እኔ ዕድል ፈንታየ ሁኖ ያልታደልሁ ሁኘ
የወፍታው እኼን አሰማኝ ብሎ በዐይኑ ውሃ ሞላ። እንባው እንዳይታይበት እደጅ ሲወጣ፣ አባቱ በዐይናቸው ተከተሉት።
“ያቺ አያትየው ኸደብተሮቹ ነው ውሎዋ። ኸተኙበት ቀባብታቸው
ይሆናል ይላል ድፍን ቋራ” አሉ ወይዘሮ ጌጤነሽ፣ አገልጋይዋ ራት
እንድታቀርብ በእጃቸው ምልክት እይሰጡ።
“ድፍን ቋራ ኸምኔው ሰምቶ ነው እኼን ሁሉ ሚለው? አንቺና
ጓደኞችሽ ጓሮ ሁናችሁ ያቦካችሁት ነው እንጂ። ለነገሩ ልዥቱ
ምንም አይወጣላት። ደማም... ቆፍጣና... ይገባታል፤ ይገባታል ::
ሚገባትን ነው ያገኘች። እኔ ለተክለሃይማኖት ተዋጋህ እየተባልሁ ስወቀስ የተክለሃይማኖትን ወንድም በካፋን አገባች?” አሉ ባላምባራስ፣
በመገረም ራሳቸውን እየነቀነቁ።
አገባች! እርምዎን ያውጡ እንግዲህ! በርሶው አጓጉል ጠባይ ነው እኼ ሁሉ የመጣው። እርስዎንስ ይበልዎ፣ ልጄን ጎዱብኝ እንጂ አሉ ወይዘሮ ጌጤነሽ፤ ለራሳቸው። ጮክ ብለው ሊናገሩ ፈለጉና በማታ ኸሳቸው ጋር ምን አጫጫኸኝ ብለው፣ “ኸቤታቸው ንግርት አለ ይባላል። ዘመዳቸው የሆነ ሰው ኸወለቴ ግንባር ጠሐይ ስትወጣ አይቷል” አሉ።
ባላምባራስ መልስ አልሰጧቸውም። ቁጭት ላይ ናቸው። ልዥህን ለልዤ ስባባል ቆይቶ፣ በትንሽ ነገር ኸጥብቅ ወዳጄ ተቀያይሜ፣ አሁን
እኼው ሌላ...ያውም ንጉሥ ወሰዳት። እንግዲህ ኸንጉሥ መንጋጋ አላስጥላት! ያቺ ቀን እንዴት ያለች የተረገመች ናት አሉ፣ ግራዝማች መንበርን የተቀየሙበትን ቀን አስታውሰው።
የጊዮርጊስ ማኅበር ነው። ግራዝማች መንበር ቤት ይበላል፤ ይጠጣል። ጨዋታው ደምቆ፣ እንደወትሮው ስለ ጦር ሜዳ ጀግንነት ይወሳል። ባላምባራስ ሁነኝ ራሳቸውን እንደ ጀግና ቢቆጥሩም፣ ስለ ጦር ሜዳ
ሲወራ አይወዱም።ከዚህ በፊት ሰድበውት የሚያውቁት ደብተራ ሞቅ ብሎታል። “አሁን በወፍታው ኸጦር ሜዳ ቋንጃውን የተመታ ዠግና ይባላል?” ብሎ በሳቅ
ተንተከተከ።
ማንም አልሳቀ። ሁሉም አንገቱን ደፋ። ሳቅና ቁም ነገር የሰፈነበት
ስብስብ ወደ መሸማቀቅ ተለወጠ።
ደብተራው የሳቀለት ሲጠፋ፣ “እኛ ባገራችን ምናቀው ሰው ቋንጃውን
ሚመታው ሲሸሽ ነው” አለ፣ የፌዝ ሳቅ እየሳቀ።
ባላምባራስ ከዓመታት በፊት ቋንጃቸውን ተመትተው ያነክሳሉና
እሳቸውን ሊነካ መሆኑን አውቀው ከተቀመጡበት ተነሥተው
ከዘራቸውን እየወዘወዙ፣ “አንት መተተኛ ደብተራ። እኔ ሁነኝ በንዳንተ ያለ ድግምተኛ አልሽረደድም። የት አባህ ጦር ሜዳ ውለህ ታውቃለህና
ስለ ጦር ሜዳ ታወራለህ? ጋን እያሸተትህ ኸድግስ ድግስ ዙር እንጂ።
ጥፋተኛው አንተ ሳትሆን አንተን ኸሰው መኻል የቀላቀለህ ነው” ብለው ከዘራቸውን ግራዝማች መንበር ላይ እየወዘወዙ፣ “መንበር አሰደብኸኝ ...
ያውም በዝህ በድውይ። ግድ የለም። እንዲህ ኻሰደብኸኝ ወዲያ እመቃብሬ እንዳትቆም... ኸዚህ ያላችሁ ሁሉ ቃሌን ቃል እንድትሉ”
ብለው እያነከሱ ወጡ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ የግራዝማችና የባላምባራስ የረጅም ዘመን ጓደኝነት አከተመ፣ አብሮም የጥላዬና የወለተጊዮርጊስ ዕጮኛነት። ባላምባራስ፣
“በቤቱ አሰደበኝ” ብለው ቂም ያዙ። ግራዝማች፣ “ደብተራው ለሰደበው እኔ ምን አረግሁ?” ብለው ቅር ተሰኙ። አስታራቂ መሃከላቸው ቢገባ ባላምባራስ፣ “ሙቼ ነው ቁሜ ኸሱ ጋር ምታረቅ” አሉ። “ልዥህን
ለልጄ” የተባባሉት ጓደኛሞች ተቀያየሙ።
ግራዝማች መንበር፣ ሁነኝ ምንም ቢሆን የረጅም ጊዜ ወዳጄ ነውና
አንድ ቀን እንታረቅ ይሆናል እያሉ የወለተጊዮርጊስን እጅ ለጠየቀ ሁሉ አይሆንም እያሉ መለሱ።
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....“ጉድ! ጉድ!” አለ፣ ወይዘሮ ጌጤነሽ ሳይቀደሙ ለመቅደም። ቆመው እጅና እግራቸውን በእርጥብ እጃቸው ያባብሳሉ።
ባላምባራስ ዝም አሉ።
ወይዘሮ ጌጤነሽ ባላቸው፣ “ምንድርነው?” ሳይሏቸው በመቅረታቸው ቅር ተሰኙ። ወሬውን ለማውራት የነበራቸውን ጉጉት ስለአመከኑባቸው
ወሽመጣቸው ተቆረጠ። የባላቸውን ዝምታ አሰቡና ነገሩ ከነከናቸው።.
“ምንድርነውም አይሉ?” አሏቸው፣ የጎሪጥ እያይዋቸው።
“የትም አምሽተሽ መተሽ ደሞ ጉድ ትያለሽ?” አሉ፣ ባላምባራስ።
“ነገረኛ፣ ታሞ አይተኛ አሉ” አሉ፣ ወይዘሮ ጌጤነሽ፣ ድምፃቸውን
ዝቅ አድርገው።
“ምን አልሽ?”
“ምን እላለሁ ሳናግርዎ መልስ አይሰጡም ወይ ነው ያልሁት። ሌላ ምን እላለሁ?” አሉ፣ ራት ለመሥራት ምድጃ ላይ ድስት የጣደችውን የቤት አገልጋይ እያዩ።
“ሚሰማሽ ካገኘሽ ምላስሽ ረዥም ነው።”
“ኸርሶ አይበልጥ” አሉ፣ አሁንም ቀስ ብለው።
ባላምባራስ ቆጣ ብለው፣ “ምን አልሽ?” ካሉ በኋላ፣ ጉድ ከሰሙ
ስለ ሰነበቱ ጉዱን የመስማት ፍላጎት አደረባቸው። ቁጣቸውን ገታ አድርገው፣ “እና ምንድርነው ጉዱ?” አሉ፣ ለጠጥ ብለው እምብዛም ለወሬ የጓጉ እንዳይመስሉ።
ወይዘሮ ጌጤነሽ እንዳልሰማ ዝም አሉ፤ እንደ ማኩረፍ አድርጓቸዋል።
“ምንድርነው ጉዱ አልሁሽ እኮ” አሉ ባላምባራስ፣ ቆጣ ብለው።
ወይዘሮ ጌጤነሽ አሁንም ያልሰሙ መሰሉ።
“ሳናግርሽ መልስ 'ማሰጪ?” የባላምባራስ ቁጣ እየተጋጋለ ነው።
“ምን አሉኝ?” አሉ ወይዘሮ ጌጤነሽ። ፊታቸው ላይ ስስ ፈገግታ ይነበባል። ዛሬ አነስተኛ ቢሆንም ባላቸው ላይ ድል ተቀዳጅተዋል።
እነዚህን መሳይ ጥቃቅን ድሎች ናቸው አንዳንዴ ባላቸውን ያሸነፉ
እንዲመስላቸው የሚያደርጓቸው።
“ጉድ እያልሽ ገባሽ። ምንድርነው ብልሽ አለመጥሽ።” አሁንም
ድምፃቸው ገኗል፣ ባላምባራስ ሁነኝ።
“አልሰማሁ ሁኜ ነው” አሉ፣ ወይዘሮ ጌጤነሽ። የባላቸው ቁጣ
የሚገነፍልበትን አፍታ ስለሚያውቁ ያገኙትን ድል እያጣጣሙ፣
“የግራማች ልዥ ...” ሲሉ ጀመሩ።
“ግራማች?” ሲሉ አቋረጧቸው፣ ባላምባራስ። ወሬውን ለመስማት
ቸኩለዋል።
“ግራማች መንበር ናቸዋ።”
“ኸሷው ጋር ስታወሪ እንደቆየሽ አውቄያለሁ። ወልደልዑል ምንን
ሆነ?”
“ሴቷ ወለቴ።”
ጥላዬ፣ የሆነ ነገር እንዳለ ደመነፍሱ ነገረው። ነፍሱ ከዳችው። ጉዱን ለመስማት ቤት ውስጥ መግባት ፈልጎ፣ ወገቡ አልታዘዝ፣ ጉልበቱ አልንቀሳቀስ አለው። እንደምንም ብሎ ተነስቶ ውስጥ ገብቶ መደብ
ላይ ተቀመጠ።
ባላምባራስ በመገረም ተመለከቱት። እሳቸው ሳይተኙ ቤት ውስጥ ስለማይገባ፣ ዐይኑን ካዩት ከርመዋል። ሆዳቸው ተገላበጠ።
“እና ምንን ሆነች?” አሉ፣ መባባታቸው እንዳይታወቅባቸው
እየታገሉ።
ወይዘሮ ጌጤነሽ ከመናገር ተቆጠቡ። ጥላዬን ሰረቅ አድረገው አዩት።እሱ የሚሉትን ለመስማት ቢጓጓም ጎንበስ ብሎ መሬቱን በስንጥር መጫጫር ጀመረ።
“ዛሬ ምንን ነክቶሻል? ምንን ሆነች ስልሽ መልስ ማሰጪ?”
“በያ ሰሞን ንዳድ ይዟቸው ኸነሱ ዘንድ ተኝተው የነበሩት ለካስ
ንጉሡ ኑረዋል...”
“ንጉሠ?”
“አዎ።”
“አጤ በካፋ?”
“እሳቸው። ሌላ ንጉሥ አለ?”
“ምንድርነው ምታወሪው?” አሉ ባላምባራስ፣ የሚስታቸውን ትንኮሳ
ችላ ብለው።
መንን
“አጤ በካፋ ራሳቸው። ወለቴ አስታማቸው ስታበቃ ዛሬ ሰዎች
ኸጥሎሽ ጋር ሰደዱ።”
“ሊያገቧት?”
“ኋላ?”
ጥላዬ ዱብ ዕዳ ሆነበት፣ ድንጋጤ ሰውነቱን አብረከረከው። ተነስቶ
ሊወጣ ፈልጎ ወሬ ለመስማት ተቀመጠ።
“ሰው ለማንጓጠጥ ማን ብሎሽ። ወረኛ! ደሞ ማታመጪው የለ” አሉ
ባላምባራስ፣ ተደናግጠዋል፣ ንዴትም ተናንቋቸዋል።
“እንዴት በሉ? ምን ያልሆነ አምጥቸ አውቃለሁ? ኸመሽ አገር ሁሉ ሚያወራው እኼንኑ ማዶል? የጣ ፈንታ ነገር ይገርማል።”
“ውነት ነው፤ ዕጣ ፈንታ ነው” አለ ጥላዬ፣ የሞት ሞቱን። ሰውነቱ
እየራደ ነው። ለራሱ፣ እኔ ዕድል ፈንታየ ሁኖ ያልታደልሁ ሁኘ
የወፍታው እኼን አሰማኝ ብሎ በዐይኑ ውሃ ሞላ። እንባው እንዳይታይበት እደጅ ሲወጣ፣ አባቱ በዐይናቸው ተከተሉት።
“ያቺ አያትየው ኸደብተሮቹ ነው ውሎዋ። ኸተኙበት ቀባብታቸው
ይሆናል ይላል ድፍን ቋራ” አሉ ወይዘሮ ጌጤነሽ፣ አገልጋይዋ ራት
እንድታቀርብ በእጃቸው ምልክት እይሰጡ።
“ድፍን ቋራ ኸምኔው ሰምቶ ነው እኼን ሁሉ ሚለው? አንቺና
ጓደኞችሽ ጓሮ ሁናችሁ ያቦካችሁት ነው እንጂ። ለነገሩ ልዥቱ
ምንም አይወጣላት። ደማም... ቆፍጣና... ይገባታል፤ ይገባታል ::
ሚገባትን ነው ያገኘች። እኔ ለተክለሃይማኖት ተዋጋህ እየተባልሁ ስወቀስ የተክለሃይማኖትን ወንድም በካፋን አገባች?” አሉ ባላምባራስ፣
በመገረም ራሳቸውን እየነቀነቁ።
አገባች! እርምዎን ያውጡ እንግዲህ! በርሶው አጓጉል ጠባይ ነው እኼ ሁሉ የመጣው። እርስዎንስ ይበልዎ፣ ልጄን ጎዱብኝ እንጂ አሉ ወይዘሮ ጌጤነሽ፤ ለራሳቸው። ጮክ ብለው ሊናገሩ ፈለጉና በማታ ኸሳቸው ጋር ምን አጫጫኸኝ ብለው፣ “ኸቤታቸው ንግርት አለ ይባላል። ዘመዳቸው የሆነ ሰው ኸወለቴ ግንባር ጠሐይ ስትወጣ አይቷል” አሉ።
ባላምባራስ መልስ አልሰጧቸውም። ቁጭት ላይ ናቸው። ልዥህን ለልዤ ስባባል ቆይቶ፣ በትንሽ ነገር ኸጥብቅ ወዳጄ ተቀያይሜ፣ አሁን
እኼው ሌላ...ያውም ንጉሥ ወሰዳት። እንግዲህ ኸንጉሥ መንጋጋ አላስጥላት! ያቺ ቀን እንዴት ያለች የተረገመች ናት አሉ፣ ግራዝማች መንበርን የተቀየሙበትን ቀን አስታውሰው።
የጊዮርጊስ ማኅበር ነው። ግራዝማች መንበር ቤት ይበላል፤ ይጠጣል። ጨዋታው ደምቆ፣ እንደወትሮው ስለ ጦር ሜዳ ጀግንነት ይወሳል። ባላምባራስ ሁነኝ ራሳቸውን እንደ ጀግና ቢቆጥሩም፣ ስለ ጦር ሜዳ
ሲወራ አይወዱም።ከዚህ በፊት ሰድበውት የሚያውቁት ደብተራ ሞቅ ብሎታል። “አሁን በወፍታው ኸጦር ሜዳ ቋንጃውን የተመታ ዠግና ይባላል?” ብሎ በሳቅ
ተንተከተከ።
ማንም አልሳቀ። ሁሉም አንገቱን ደፋ። ሳቅና ቁም ነገር የሰፈነበት
ስብስብ ወደ መሸማቀቅ ተለወጠ።
ደብተራው የሳቀለት ሲጠፋ፣ “እኛ ባገራችን ምናቀው ሰው ቋንጃውን
ሚመታው ሲሸሽ ነው” አለ፣ የፌዝ ሳቅ እየሳቀ።
ባላምባራስ ከዓመታት በፊት ቋንጃቸውን ተመትተው ያነክሳሉና
እሳቸውን ሊነካ መሆኑን አውቀው ከተቀመጡበት ተነሥተው
ከዘራቸውን እየወዘወዙ፣ “አንት መተተኛ ደብተራ። እኔ ሁነኝ በንዳንተ ያለ ድግምተኛ አልሽረደድም። የት አባህ ጦር ሜዳ ውለህ ታውቃለህና
ስለ ጦር ሜዳ ታወራለህ? ጋን እያሸተትህ ኸድግስ ድግስ ዙር እንጂ።
ጥፋተኛው አንተ ሳትሆን አንተን ኸሰው መኻል የቀላቀለህ ነው” ብለው ከዘራቸውን ግራዝማች መንበር ላይ እየወዘወዙ፣ “መንበር አሰደብኸኝ ...
ያውም በዝህ በድውይ። ግድ የለም። እንዲህ ኻሰደብኸኝ ወዲያ እመቃብሬ እንዳትቆም... ኸዚህ ያላችሁ ሁሉ ቃሌን ቃል እንድትሉ”
ብለው እያነከሱ ወጡ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ የግራዝማችና የባላምባራስ የረጅም ዘመን ጓደኝነት አከተመ፣ አብሮም የጥላዬና የወለተጊዮርጊስ ዕጮኛነት። ባላምባራስ፣
“በቤቱ አሰደበኝ” ብለው ቂም ያዙ። ግራዝማች፣ “ደብተራው ለሰደበው እኔ ምን አረግሁ?” ብለው ቅር ተሰኙ። አስታራቂ መሃከላቸው ቢገባ ባላምባራስ፣ “ሙቼ ነው ቁሜ ኸሱ ጋር ምታረቅ” አሉ። “ልዥህን
ለልጄ” የተባባሉት ጓደኛሞች ተቀያየሙ።
ግራዝማች መንበር፣ ሁነኝ ምንም ቢሆን የረጅም ጊዜ ወዳጄ ነውና
አንድ ቀን እንታረቅ ይሆናል እያሉ የወለተጊዮርጊስን እጅ ለጠየቀ ሁሉ አይሆንም እያሉ መለሱ።
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...ካንድ ስምንት ቀን በኋላ፣ ማታ ተመስገን ክፍል ቁጭ ብዬ
ስስራ፣ ተመስገን መጣና አልጋው ላይ ዘጭ ብሉ ተጋደመ፡፡ እፎይ!
ብሎ ተነፈሰ
«ሲኒማ የገባችሁ መስሉኝ» አልኩት
«ሌሎቹ ገቡ፣ እኔ ግን ተውኩት»
«ለምን ተውከው?» አልኩት። ድምፄ «አንተ ተንኮለኛ!»
እንደሚል አይነት ነበር
«ደስ አላለኝማ!» አለኝ፡፡ ትንንሽ አይኖቹ ሊደበቁ ጀምረዋል፣
ግን ጥርሶቹ ገና መታየት አልጀመሩም
«ውሸታም! ቀጠሮ ቢኖርህ ነው እንጂ» አልኩት
«ከማን ጋር?»
«እኔ አውቃለሁ እንዴ ያንተን ተንኮል? ወይ ካንዷ ብሎንድ
(ፀጉሯ ብጫ ወይም ነጭ ብጤ) ጋር፣ ወይ ከሲልቪ ጋር»
«ሲልቪ!? አላወቅክምና!»
«ምን?»
«ቀርቶ!»
«ምነዋ?»
«ምን እባክህ የሴት ነገር» አለ «አገር ጤና ብዬ እንደ ሁልጊዜያችን ወዲህ አመጣሁዋት፡፡ ከሰአት በኋላ ነበር። የከሰአት በኋላው እንዴት እንደሚጣፍጥ ታውቅ የለ? ልብሷን አወላለቀችና
አልጋው ውስጥ ገባች። እየተንገበገብኩ ተከትያት ልገባ ስል፣
ከትራሱ ላይ ኣንዲት ፀጉር እንስታ አቀበለችኝ። ረዥም የፈረንጅ
ፀጉር ነው፤ ግን ጥቁር አይደለም፣ ቡና አይነት ነው»
«ይሄ የኔ ፀጉር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ አለችኝ»
«ዝም ኣልኩ። አልገባኝም አየህ
«ተናገር እንጂ» አለችኝ። እግዜር ያሳይህ፡፡ በመጀመሪያ
አልጋው ውስጥ ልገባ ጎምበስ እንዳልኩ ኣሁንም አለሁ፡፡ ይታይሀል? ራቁቴን አልጋው ላይ ባራት እግሬ ቆሜ? እንደሚድህ ልጅ:: ልብሷን ስታወልቅ እያየሁና የሚጠብቀኝን ደስታ እያሰብኩ ግትር አድርጎ ቅንዝር ወጥሮኛል፡፡»
የተመስገን አይኖች ጨርሰው ጠፉ፣ ጥርሶቹ ተገለጡ፣ ይሰቅ
ጀመር፡፡ ከት ብሎ እየሳቀ፣ ሳቅ በሚቆራርጠው ንግግር
ገና አሁን ታየኝ ሀ! ሀ! ሀ! እንዴት እንዴት - ሀ! ሀ! U! እንዴት እንደነበርኩ ሁ! ሁ! ሁ! አንዲህ ነበርኩ» አለና በጀርባው ከተጋደመበት ተነስቶ ዞሮ በጉልበቱና በእጁ ተንበረከከ፡፡
ከስሩ ትራሱን አስተካከለና፣ ሌባ ጣቱን እያነጣጠረበት
«እኔ እንዲሀ ነኝ፣ ሂሂ!!» ትራሱን «እቺ ሲልቪ ናት።
ያቀበለችኝን ፀጉር ባንድ እጄ እንደዚህ ይዣለሁ። እንዳትበጠስ
ወይም ወድቃ እንዳትጠፋ እየተጠነቀቅኩ፣ ያቺን ነጃሳ ፀጉር እንዲህ ይዣለሁ። ቁላዬ ደሞ እዚህ ጋ ቆሞ ሲልቪን ቁልቁል ያያታል።አይ የኔ ቁላ! ቂል ነውኮ፡፡ ያንተም ቂል ነው?» እንደገና ሳቅ
አሸነፈው። አልጋው ላይ ተንከባለለ። ሳቁ ሲያልፍለት
«በኋላስ?» አልኩት
«በኋላማ ምን ልበልህ ልጄ? ቃል ሳትናገር ተነስታ ልብሷን
መልሳ ለበሰች፡፡ ረጋ ባለ ድምፅ 'የኔና ያንተ ነገር በዚሁ አለቀ”
ብላኝ ልትወጣ ስትል፣ እኔ እዚች ጋ ራቁቴን እንደቆምኩ
«ምን ነካሽ?» አልኳት፡፡ ሲያቀብጠኝ'ኮ ነው:: እስቲ ዝም ብላትስ?
«ዘወር አለችና፣ እሱ ጠረጴዛ ላይ ያለውን መፃህፍትና ደብተር
በአጇ አንዴ ገፍታ መሬት ላይ አዝረከረከችው:: እና ጠረጴዛውን
በተጨበጠ እጇ ደጋግማ እየመታች
«እኔ የእስላም ሀሪም ሴት - አይደለሁም!» ብላኝ ስታበቃ፣ ወጥታ በሩን በሀይል ጓ! አርጋው ሄደች። ልብሴን ልለብስ
ካናቴራዬን ሳነሳ በሩ ብርግድ ብሎ ተከፈተ። ማን ገባ መሰለህ?»
አለኝ
«ማን?» አልኩት
«ሲልቪ ራሷ ነቻ! የሴት ነገር! ከመቼው ሀሳቧን ለወጠች?!
እያልኩ ልገረም ስጀምር፣ ኣጠገቤ መጣች። አቅፋ ልትስመኝ
እንደሆነ ገባኝ፡፡ ትንሽ ልኮራባት አሰብኩ። ታድያ እሷ ምን አረገች
መሰለህ? እወቅ : ስቲ።»
«በጥፊ መታችህ?»
«ብጭራሽ!»
«አቅፋ ሳመችህ?»
«ትቀልዳለህ?»
«እንግዲያው ምን አረገች?» አልኩት
«ጫማዋን አረገች»
«ምን?»
«በንዴት ጫማዋን ረስታው ሄዳ ነበር፡፡ ተመልሳ አረገችውና
ወጣች። እኔ ራቁቴን ቆሜ ቀረሁ፡፡ ቁላዬ እስካሁን ተኝቷል፡፡ ከዚያ
በኋላ አናግራኝ አታውቅም»
«ጥፋቱ ያንተ ነው» አልኩት
«እንዴት?» አለኝ
«ያመጣሀቸው ሴቶች ሊሄዱ ሲሉ «ፀጉሮችሽን ሁሉ ይዘሻል?
ቁጠሪ እስቲ ለምን አትላቸውም?» አልኩት
«መቼ ሴት አመጣሁና?» አለኝ
«እ-ህ? ቡናማው ፀጉርሳ?»
«ከየት እንደመጣ እንጃለት:: ምናልባት ቤት የምትጠርገው
አልጋ የምታነጥፈው አሮጊት ያን እለት ታማ ኖሮ፣ በሷ ምትክ
ባለቡናማ ፀጉር ሴት አልጋዬን አንጥፋልኝ ይሆናል»
«ምስኪን ተመስገን!» አልኩት
ምስኪን ትላለህ ምስኪን። ይኸው እስከዛሬ ዖም ላይ እገኛለሁ
«ዛሬ ማታ ግን ለመግደፍ ያሰብክ ትመስላለህ»
«ነበር እባክህን። ፀጉሯን እንደ ወንድ ነው 'ምትቆርጠው፣
ቢሆንም ምንም አትል። ብቻ »
«ብቻ ምን?»
«የት እንደምወስዳት ጨንቆኛል»
ሲመሽ ፈረንሳዮች concierge
የሚሉት ዘበኛ ይመጣና' ወደመኝታ ቤቶቹ የሚያስገባው በር አጠገብ አንዲት ቢሮ አለችው፣ እዚያች ቁጭ ብሉ ወጪ ገቢውን ሁሉ ይመለከታል። ወንዶች መኝታ ቤት ሴት ማስገባት ክልክል ነው፡፡)
«የኔ ሆቴል አለልህ አይደለም እንዴ?» አልኩት
«አትጠቀምበትም?»
«እዚህ ልተኛ እችላለሁ»
እሱማ ጥሩ ነበር»
“ብቻ እንዳታስጮሀት አደራ፡፡ ካስጮህካትም ፎጣ አጉርሳት።
ብዬ የሆቴሌን ቁልፍ ሰጠሁት
ተመስገን ወደ ቀጠሮው ከሄደ በኋላ ተመልሼ ልስራ
በጠበጠኝ። ተነስቼ አሜሪካዊቷ ቤት ሄድኩ፡፡ ጉዳዬን አስረዳኋት።
አልቻልኩም፡፡ ሲልቪ ለኔ ስትል እንደተወችው ገባኝ፡፡ ይህ ሀሳብ
ከዚህ በፊት አገሬ እጮኛ አለችኝ ብያት ነበር፡፡ አሁን፣ እጮኛዬ
ካንቺ ጋር ያለኝን ግንኙነት አወቀች፡፡ ማን እንደነገራት እንጃ፡
ወረቀት ፃፈችልኝ። በአንድ ሳምንት ውስጥ ኣሜሪካንህን ትተሀታል
የሚል ወሬ ካልደረሰኝ ሌላ እኛ ፈልግ አለችኝ፣ ብዬ ነገርኳት።
«i derstand የዚህ መጥፎ ዜና ምክንያት በመሆኔ በጣም
አዝናለሁ» አለችኝ። ያቀድኩት ይህን ነግሬያት ደህና እደሪ ብያት
ሲልቪን ፍለጋ ለመሄድ ነበር። ግን ልጅቱ ጥቁር ስስ የሌሊት ልብስ
ለብሳ ስትራመድ በጣም ታስጎመጃለች፣ ገላዋን ታጥባ ቆዳዋን በታልከም ዱቄት አሻሽታው፣ ሽታው ይማርካል፡፡ ከሷ ጋር አደርኩ
«ራሷን በጣም ታዘብኩት። በጣም ፀፀት ተሰማኝ፣ ሲልቪን
የበደልኳት መሰለኝ»
በነጋታው ሲልቪን ከምግብ ቤት ስትወጣ ጠብቄ ኣገኘኋት።
ቡና ልጋብዝሽ አልኳት። ኤክስ ውስጥ የምወደው ካፌ የለኝም
አልኩህ? አለችኝ፣ እሺ ማርሰይ ልውሰድሽ አልኳት። መኪናዬ
ጋራዥ ናት አለችኝ፡፡ በኦቶቡስ ልውሰድሽ አልኳት። አልፈልግም
አለችኝ። እንግዲያው ምን እናርግ? አልኳት፡፡ እኔ ቡና ላጠጣህ፣ራሴ አፍልቼ፣ አለችኝ፡፡ ቤቷ ወሰደችኝ፣ ከኤክስ ትንሽ ወጣ ብሎ ባላገሩ ውስጥ ነው
«የሴዛን የነበረው ቤት በዚህ በኩል ነው። መሄድ ትፈልጋለህ?»
አለችኝ
«አልፈልግም» አልኳት
«እኔም ሄጀ አላውቅም» አለችኝ
እየሳቅኩ «Tut'en fous, ch?» አልኳት («ደንታ የለሽም፣ እ?»)
እየሳቀች፣ «Je m'en fous eperdument!» አለችኝ («እቺን ያህል እንኳ ደንታ የለኝም»)
ቤቷ ገባን። ሁለት ክፍል (አንድ መኝታ፣ አንድ ሳሎን) ወጥ
ቤት፣ መታጠቢያ ክፍል። በየግድግዳው የልዩ ልዩ አቢይ ስእሎች እትም ተለጥፏል። የቤት እቃው ዘመናዊ ነው፣ ሰማያዊና ወይን ጠጅ ቀለማት ይበዙበታል
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...ካንድ ስምንት ቀን በኋላ፣ ማታ ተመስገን ክፍል ቁጭ ብዬ
ስስራ፣ ተመስገን መጣና አልጋው ላይ ዘጭ ብሉ ተጋደመ፡፡ እፎይ!
ብሎ ተነፈሰ
«ሲኒማ የገባችሁ መስሉኝ» አልኩት
«ሌሎቹ ገቡ፣ እኔ ግን ተውኩት»
«ለምን ተውከው?» አልኩት። ድምፄ «አንተ ተንኮለኛ!»
እንደሚል አይነት ነበር
«ደስ አላለኝማ!» አለኝ፡፡ ትንንሽ አይኖቹ ሊደበቁ ጀምረዋል፣
ግን ጥርሶቹ ገና መታየት አልጀመሩም
«ውሸታም! ቀጠሮ ቢኖርህ ነው እንጂ» አልኩት
«ከማን ጋር?»
«እኔ አውቃለሁ እንዴ ያንተን ተንኮል? ወይ ካንዷ ብሎንድ
(ፀጉሯ ብጫ ወይም ነጭ ብጤ) ጋር፣ ወይ ከሲልቪ ጋር»
«ሲልቪ!? አላወቅክምና!»
«ምን?»
«ቀርቶ!»
«ምነዋ?»
«ምን እባክህ የሴት ነገር» አለ «አገር ጤና ብዬ እንደ ሁልጊዜያችን ወዲህ አመጣሁዋት፡፡ ከሰአት በኋላ ነበር። የከሰአት በኋላው እንዴት እንደሚጣፍጥ ታውቅ የለ? ልብሷን አወላለቀችና
አልጋው ውስጥ ገባች። እየተንገበገብኩ ተከትያት ልገባ ስል፣
ከትራሱ ላይ ኣንዲት ፀጉር እንስታ አቀበለችኝ። ረዥም የፈረንጅ
ፀጉር ነው፤ ግን ጥቁር አይደለም፣ ቡና አይነት ነው»
«ይሄ የኔ ፀጉር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ አለችኝ»
«ዝም ኣልኩ። አልገባኝም አየህ
«ተናገር እንጂ» አለችኝ። እግዜር ያሳይህ፡፡ በመጀመሪያ
አልጋው ውስጥ ልገባ ጎምበስ እንዳልኩ ኣሁንም አለሁ፡፡ ይታይሀል? ራቁቴን አልጋው ላይ ባራት እግሬ ቆሜ? እንደሚድህ ልጅ:: ልብሷን ስታወልቅ እያየሁና የሚጠብቀኝን ደስታ እያሰብኩ ግትር አድርጎ ቅንዝር ወጥሮኛል፡፡»
የተመስገን አይኖች ጨርሰው ጠፉ፣ ጥርሶቹ ተገለጡ፣ ይሰቅ
ጀመር፡፡ ከት ብሎ እየሳቀ፣ ሳቅ በሚቆራርጠው ንግግር
ገና አሁን ታየኝ ሀ! ሀ! ሀ! እንዴት እንዴት - ሀ! ሀ! U! እንዴት እንደነበርኩ ሁ! ሁ! ሁ! አንዲህ ነበርኩ» አለና በጀርባው ከተጋደመበት ተነስቶ ዞሮ በጉልበቱና በእጁ ተንበረከከ፡፡
ከስሩ ትራሱን አስተካከለና፣ ሌባ ጣቱን እያነጣጠረበት
«እኔ እንዲሀ ነኝ፣ ሂሂ!!» ትራሱን «እቺ ሲልቪ ናት።
ያቀበለችኝን ፀጉር ባንድ እጄ እንደዚህ ይዣለሁ። እንዳትበጠስ
ወይም ወድቃ እንዳትጠፋ እየተጠነቀቅኩ፣ ያቺን ነጃሳ ፀጉር እንዲህ ይዣለሁ። ቁላዬ ደሞ እዚህ ጋ ቆሞ ሲልቪን ቁልቁል ያያታል።አይ የኔ ቁላ! ቂል ነውኮ፡፡ ያንተም ቂል ነው?» እንደገና ሳቅ
አሸነፈው። አልጋው ላይ ተንከባለለ። ሳቁ ሲያልፍለት
«በኋላስ?» አልኩት
«በኋላማ ምን ልበልህ ልጄ? ቃል ሳትናገር ተነስታ ልብሷን
መልሳ ለበሰች፡፡ ረጋ ባለ ድምፅ 'የኔና ያንተ ነገር በዚሁ አለቀ”
ብላኝ ልትወጣ ስትል፣ እኔ እዚች ጋ ራቁቴን እንደቆምኩ
«ምን ነካሽ?» አልኳት፡፡ ሲያቀብጠኝ'ኮ ነው:: እስቲ ዝም ብላትስ?
«ዘወር አለችና፣ እሱ ጠረጴዛ ላይ ያለውን መፃህፍትና ደብተር
በአጇ አንዴ ገፍታ መሬት ላይ አዝረከረከችው:: እና ጠረጴዛውን
በተጨበጠ እጇ ደጋግማ እየመታች
«እኔ የእስላም ሀሪም ሴት - አይደለሁም!» ብላኝ ስታበቃ፣ ወጥታ በሩን በሀይል ጓ! አርጋው ሄደች። ልብሴን ልለብስ
ካናቴራዬን ሳነሳ በሩ ብርግድ ብሎ ተከፈተ። ማን ገባ መሰለህ?»
አለኝ
«ማን?» አልኩት
«ሲልቪ ራሷ ነቻ! የሴት ነገር! ከመቼው ሀሳቧን ለወጠች?!
እያልኩ ልገረም ስጀምር፣ ኣጠገቤ መጣች። አቅፋ ልትስመኝ
እንደሆነ ገባኝ፡፡ ትንሽ ልኮራባት አሰብኩ። ታድያ እሷ ምን አረገች
መሰለህ? እወቅ : ስቲ።»
«በጥፊ መታችህ?»
«ብጭራሽ!»
«አቅፋ ሳመችህ?»
«ትቀልዳለህ?»
«እንግዲያው ምን አረገች?» አልኩት
«ጫማዋን አረገች»
«ምን?»
«በንዴት ጫማዋን ረስታው ሄዳ ነበር፡፡ ተመልሳ አረገችውና
ወጣች። እኔ ራቁቴን ቆሜ ቀረሁ፡፡ ቁላዬ እስካሁን ተኝቷል፡፡ ከዚያ
በኋላ አናግራኝ አታውቅም»
«ጥፋቱ ያንተ ነው» አልኩት
«እንዴት?» አለኝ
«ያመጣሀቸው ሴቶች ሊሄዱ ሲሉ «ፀጉሮችሽን ሁሉ ይዘሻል?
ቁጠሪ እስቲ ለምን አትላቸውም?» አልኩት
«መቼ ሴት አመጣሁና?» አለኝ
«እ-ህ? ቡናማው ፀጉርሳ?»
«ከየት እንደመጣ እንጃለት:: ምናልባት ቤት የምትጠርገው
አልጋ የምታነጥፈው አሮጊት ያን እለት ታማ ኖሮ፣ በሷ ምትክ
ባለቡናማ ፀጉር ሴት አልጋዬን አንጥፋልኝ ይሆናል»
«ምስኪን ተመስገን!» አልኩት
ምስኪን ትላለህ ምስኪን። ይኸው እስከዛሬ ዖም ላይ እገኛለሁ
«ዛሬ ማታ ግን ለመግደፍ ያሰብክ ትመስላለህ»
«ነበር እባክህን። ፀጉሯን እንደ ወንድ ነው 'ምትቆርጠው፣
ቢሆንም ምንም አትል። ብቻ »
«ብቻ ምን?»
«የት እንደምወስዳት ጨንቆኛል»
ሲመሽ ፈረንሳዮች concierge
የሚሉት ዘበኛ ይመጣና' ወደመኝታ ቤቶቹ የሚያስገባው በር አጠገብ አንዲት ቢሮ አለችው፣ እዚያች ቁጭ ብሉ ወጪ ገቢውን ሁሉ ይመለከታል። ወንዶች መኝታ ቤት ሴት ማስገባት ክልክል ነው፡፡)
«የኔ ሆቴል አለልህ አይደለም እንዴ?» አልኩት
«አትጠቀምበትም?»
«እዚህ ልተኛ እችላለሁ»
እሱማ ጥሩ ነበር»
“ብቻ እንዳታስጮሀት አደራ፡፡ ካስጮህካትም ፎጣ አጉርሳት።
ብዬ የሆቴሌን ቁልፍ ሰጠሁት
ተመስገን ወደ ቀጠሮው ከሄደ በኋላ ተመልሼ ልስራ
በጠበጠኝ። ተነስቼ አሜሪካዊቷ ቤት ሄድኩ፡፡ ጉዳዬን አስረዳኋት።
አልቻልኩም፡፡ ሲልቪ ለኔ ስትል እንደተወችው ገባኝ፡፡ ይህ ሀሳብ
ከዚህ በፊት አገሬ እጮኛ አለችኝ ብያት ነበር፡፡ አሁን፣ እጮኛዬ
ካንቺ ጋር ያለኝን ግንኙነት አወቀች፡፡ ማን እንደነገራት እንጃ፡
ወረቀት ፃፈችልኝ። በአንድ ሳምንት ውስጥ ኣሜሪካንህን ትተሀታል
የሚል ወሬ ካልደረሰኝ ሌላ እኛ ፈልግ አለችኝ፣ ብዬ ነገርኳት።
«i derstand የዚህ መጥፎ ዜና ምክንያት በመሆኔ በጣም
አዝናለሁ» አለችኝ። ያቀድኩት ይህን ነግሬያት ደህና እደሪ ብያት
ሲልቪን ፍለጋ ለመሄድ ነበር። ግን ልጅቱ ጥቁር ስስ የሌሊት ልብስ
ለብሳ ስትራመድ በጣም ታስጎመጃለች፣ ገላዋን ታጥባ ቆዳዋን በታልከም ዱቄት አሻሽታው፣ ሽታው ይማርካል፡፡ ከሷ ጋር አደርኩ
«ራሷን በጣም ታዘብኩት። በጣም ፀፀት ተሰማኝ፣ ሲልቪን
የበደልኳት መሰለኝ»
በነጋታው ሲልቪን ከምግብ ቤት ስትወጣ ጠብቄ ኣገኘኋት።
ቡና ልጋብዝሽ አልኳት። ኤክስ ውስጥ የምወደው ካፌ የለኝም
አልኩህ? አለችኝ፣ እሺ ማርሰይ ልውሰድሽ አልኳት። መኪናዬ
ጋራዥ ናት አለችኝ፡፡ በኦቶቡስ ልውሰድሽ አልኳት። አልፈልግም
አለችኝ። እንግዲያው ምን እናርግ? አልኳት፡፡ እኔ ቡና ላጠጣህ፣ራሴ አፍልቼ፣ አለችኝ፡፡ ቤቷ ወሰደችኝ፣ ከኤክስ ትንሽ ወጣ ብሎ ባላገሩ ውስጥ ነው
«የሴዛን የነበረው ቤት በዚህ በኩል ነው። መሄድ ትፈልጋለህ?»
አለችኝ
«አልፈልግም» አልኳት
«እኔም ሄጀ አላውቅም» አለችኝ
እየሳቅኩ «Tut'en fous, ch?» አልኳት («ደንታ የለሽም፣ እ?»)
እየሳቀች፣ «Je m'en fous eperdument!» አለችኝ («እቺን ያህል እንኳ ደንታ የለኝም»)
ቤቷ ገባን። ሁለት ክፍል (አንድ መኝታ፣ አንድ ሳሎን) ወጥ
ቤት፣ መታጠቢያ ክፍል። በየግድግዳው የልዩ ልዩ አቢይ ስእሎች እትም ተለጥፏል። የቤት እቃው ዘመናዊ ነው፣ ሰማያዊና ወይን ጠጅ ቀለማት ይበዙበታል
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ከተማውን ጥሎ ወጣ፡፡ ከተማውን ለቅቆ ገጠር እስከገባ ድረስ እየተጣራ ነበር የሚሄደው፡፡ ወዴት እንደሚሄድ ሳያስተውል መንገድ እንደመራው ዝም እያለ ተጓዘ፡፡ ከነጋ ጀምሮ እህል አልቀመሰም:: ሆኖም የረሃብ ስሜት አልተሰማውም፡፡ ቁጣ ቁጣ ብሉታል፡፡ በማን ላይ ወይም በምን ምክንያት እንደተቆጣ ግን አያውቅም:: የሚቀጥለው ምን ይሆን ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
የገጠር አየር የልጅነት ጊዜውን አስታወሰው:: የልጅነት ዘመኑን ካስታወሰ በጣም ቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም ብዙ ኣሳቦች ተፈራረቁበት፡፡»
ፀሐይ አሽቆልቁላ ገብታ ከአድማስ ውስጥ ልትገባ ስትል ዣን ቫልዣ
እልም ካለ ጫካ ውስጥ ከአንዲት ጉብታ ላይ ቁጭ ብሎአል፡፡ የአልፕስ ተራራ በሩቁ ይታያል፡፡ ከጫካው ወጣ እንዳለ አንድ ቀጭን የእግር መንገድ አለ፡፡
ከዚህ ቁጭ ብሎ ሲያሰላስል ደስ የሚል ድምፅ ይሰማል፡፡ ፊቱን
ሲያዞር ወደ አሥራ ሁለት ዓመት የሚሆነው ልጅ እየዘመረ ወደ እርሱ ይመጣል:: ልጁ በጭንቅላቱ ሣጥን መሳይ ነገር ተሸክሞአል፡፡ ልጁ ጥቂት
ከተራመደ በኋላ ቆም ብሎ በእጁ የያዘውን ሣንቲም ወደ ሰማይ እያጎነ ይጫወታል:: የልጁ ሀብት ምናልባት ይኸው ነጭ ሽልንግ ብቻ ሳይሆን አልቀረም::
ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት ሲደርስ የሰውዬው ከእዚያ መኖር ሳይገነዘብ ቆም አለ፡፡ እንደ ልማዱ ሣንቲሙን ወደ ሰማይ አጎነ፡ ሣንቲሙ አምልጦት
ከመሬት ሊወድቅ ዣን ቫልዣ ወደ ተቀመጠበት በረረ:: ዣን ቫልዣ
ሽልንጉን በእግሩ ረግጦ ያዘበት:: የልጁ ዓይን ሣንቲሙን ተከትሎ ስለሄደ የት ላይ እንዳለ ያውቃል፡፡ ልጁ አልፈራም፤ በቀጥታ ወደ ሰውዬው ሄደ::
«ጌታዬ ገንዘቤን» አለ ልጁ የዋህነትና ድንቁርና በተሞላበት አንደበት::
«ስምህ ማነው?» ሲል ዣን ቫልዣ ጠየቀው::
«ትንሹ ዥራቪ ነው ጌታዬ::»
«ቶሉ ከዚህ ጥፋ» አለው ዣን ቫልዣ ::
«ፍራንኬስ?» ሲል ልጁ ጠየቀ፡፡
ዣን ቫልዣ እንዳቀረቀረ ቀረ::
«ገንዘቤን» አለ ልጁ እምባ እየተናነቀወ :: ሽልንጌን!»
ዣን ቫልዣ ምንም ነገር እንዳልሰማ ሰው ፀጥ አለ፡፡ ልጁ የሰውየውን ሸሚዝ ኮሌታ በአንድ እጁ ያዘ፡፡ በሌላው እጁ ሣንቲሙን ለማስለቀቅ የሰውየውን እግር ለማንሳት ሞከረ::
«ገንዘቤን እፈልጋለሁ ፧ ሽልጌን!» ብሎ ከጮኸ በኋላ ትንሹ ዠራቬ
ማልቀስ ጀመረ:: ዣን ቫልዣ አንገቱን ቀና አደረገ፡፡ ከተቀመጠበት ግን አልተነሳም:: ፊቱ፡ በአሳብ የተዋጠና የተጨነቀ ይመስላል፡፡ በመገረም ልጁን
አትኩሮ አየው:: ዱላውን ሳብ ኣድርጎ «አንተ ማነህ? እህ! ምንድነው የምትፈልገው? እስካሁን አልሄድክም እንዴ» ሲል በሚያስፈራ ድምፅ ጮኸበት:: ሣንቲሙን እንደረገጠ ከመቀመጫው ብድግ ብላ «ራስህን ብትጠብቅ ይሻልሃል» አለው::
ልጁ በፍርሃት ተወጦ ቀና ብላ አየወ:: ሰውነቱ ይንቀጠቀጥ
ጀመር፡፡ ወዲያው ከጥቂት ሰኮንድ መርበትበት በኋላ ልጁ አግሬ አውጪኝ ብሎ ሸመጠጠ፡፡ ዞር ብሎ ለማየት ወይም ጩኸት ለማሰማት እንኳን አልደፈረም፡፡ ሆኖም ጥቂት እንደተጓዘ ትንፋሽ አጥሮት ቆም አለ:: ግን ብዙ
አልቆመም፧ መንገዱን ቀጠለ፡፡
ፀሐይዋ ጠለቀች፡፡ ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት አካባቢ ብርሃን ለጨለማ ሥፍራዋን ለቀቀች:: ቀኑን መሉ ምግብ የሚሉት ነገር አልቀመሰም::ምናልባትም ትንሽ እንደትኩሳት ብጤ ሳይሞካክረው አልቀረም::
ልጁ ከሄደ ጀምሮ ከተቀመጠበት ነቅነቅ አላለም:: በኃይል ነው
የሚተነፍሰው:: ከተቀመጠበት ጥቂት ራቅ ብሎ ከነበረው የሸክላ ስባሪ ገል ላይ ዓይኑን ተከለ፡፡ ስለገሉ ይመራመር ጀመር፡፡ ግን በድንገት መላ ሰውነቱ
ተንቀጠቀጠ፡፡ የሌሊቱ ቁር እየተሰማው ሄደ፡፡
ቆቡን ሳብ አድርጎ ግንባሩን ሸፈነ:: የሸሚዙን አዝራር ለመቆለፍ
ጣቶቹ አዝራር ፍለጋ ላይ ታች አሉ:: ብድግ ብሎ ወደፊት ራመድ ካለ ከኋላ መለስ ብሉ ዱላውን ለማንሳት ጎንበስ አለ፡፡
በእግሩ ረግጦ ይዞት የነበረው ሽልንግ በማብረቅረቁ ዓይኑ ወደዚያ ተሳበ፡፡ ኮረንቲ እንደያዘው ሰው ተሸማቀቀ፡፡ «ምንድነው ነገሩ?» ሲል ጥርሱን በማፋጨት ራሱን ጠየቀ:: እንደገና ወደኋላ መለስ ብሉ ሣንቲሙን በእግሩ በመርገጥ ሸፈነው:: ሣንቲሙ ዓይን አብቅሎ የሚያየው መሰለው::
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ እግሩን መነጨቀና ጎንበስ ብሎ ሣንቲሙን
አነሳ፡፡ ቀና ብሎ አካባቢውን ተመለከተ:: ጋራውና ሸንተረሩ ሁሉ የሚያየው ስለመሰለው በፍርሃት ተውጦ መወጊያ እንደምትፈልግ ዱኮላ ዓይኑ በፍርሃት ተቅበዘበዘ፡፡ ከቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡
ምንም ነገር አላየም:: ጊዜው እየጨለመና አየሩ እጅግ እየቀዘቀዘ ሄደ:: ሰማዩ በጭጋግ ተሸፈነ፡፡
«ወይ ጣጣ» ሲል ልጁ በሄደበት አቅጣጫ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ አንድ
ሰላሳ - እርምጃ ያህል እንደተራመደ ቆም ኣለ፡፡ አካባቢውን ተመለከቱ።
ምንም ነገር የለም:: ድምፁን እጅግ ከፍ አድርጎ «ዠራቬ» ሲል ተጣራ፡፡ ከዚያም ድምፁ
አጥፍቶ አዳመጠ:: መልስ አላገኘም፡፡
አገሩ ጭር ያለና ጭጋጋም ቢሆንም አካባቢው በግልጽ ይታያል ከዝምታና ከራሱ ጥላ በስተቀር የሚንቀሳቀስ ፍጠር ጨርሶ አልነበረም ዣን ቫልዣ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የሚወስደውን እርምጃ ፍጥነት በመጨመር እንደ መሮጥ አለ። አልፎ አልፎ ቆም እያለ በሚያስፈራ ሻካራ ድምፅ «ዠራቬ» ሲል እንደገና ተጣራ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ልጁ ቢሰማው
እንኳን በፍርሃት ስለሚዋጥ ይደበቃል እንጂ መልስ አይሰጠውም:: ነገር ግን ልጁ በርግጥም በጣም ርቆ ሄዷል፡፡
ዣን ቫልዣ እንደገና ልጁ በሄደበት ኣቅጣጫ መሮጥ ጀመረ
እየተገላመጠ፣ እየጮኸ፣ እየተጣራ ብዘ ተጓዘ፡፡ ግን ማንንም አላገኘም በደረቱ ተንፏቅቆ የሚሄድ ወይም ድምፁን አጥፍቶ ያደፈጠ እየመሰለ ከአንዴም ሁለቴ፣ ከሁለቴም ሦስቴ መንገዱን ለቅቆ ወደ ጥሻው ዞር እያለ
ተመለከተ፡፡ ግን ሰው የመሰለው ነገር ጠጋ ሲል ቁጥቋጦ ወይም ድንጋ ሆኖ ያገኘዋል፡፡ በመጨረሻ ሦስት መንታ መንገዶች ከሚገናኙበት ደረሰ ከመሐል መንገድ ላይ ቆመ:: ጨረቃዋ ብቅ ብላለች:: ለማየት እስከቻለ
ድረስ አርቆ ተመለከተ:: «ዥራቬ፣ ትንሹ ዥራቬ፣ ዠራቬ» በማለት
ሦስት ጊዜ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተጣራ:: ድምፁ የገደል ማሚቶ እንኳ ሳያዕማ ከጭጋጉ ውስጥ ተውጦ ቀረ:: «ትንሹ ዥራቬ» ሲል ዝግ በደከመ ድምፅ አጉረመረመ:: ያ የመጨረሻው ሙከራ ነበር፡፡ በዓይ የማይታይ ኃይል በዱላ እንደመታው ሰው በድንገት እግሩ ተሳስሮ ጉልበቱ እጥፍጥፍ አለበት:: ፀጉሩን በእጁ ጨብጦና ፊቱን ጉልበቱ ላይ አሳርፎ
ከቋጥኝ ድንጋይ ላይ በመቀመጥ «ምን ዓይነት እድለቢስ ሰው ነኝ» አለ ጮኸ፡፡ ልቡ እያበጠ ሄደ፡፡ ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ ከአሥራ ዘጠኝ ዓመት ወዲህ ሲያለቅስ የመጀመሪያው ነበር:: ዣን ቫልዣ ብዙ አለቀሰ፡፡ ከሕፃኑ መባባትና ከሴቶች መርበትበት ይበልጥ በፍርሃት ተውጦ ከዓይኑ እምባ የወጣ እስኪመስለው ድረስ በማልቀስ አንጀቱን እርር ድብን አደረገ እያለቀሰ ሳለ ከሕሊናው ውስጥ የነበረው ብርሃን እየፈካ ሄደ፡፡
የተለየ ብርሃን ነበር፡፡ ያ ብርሃን አሳደደው፤ አስፈራራው፡፡ ያለፈው የሕይወቱ ዘመን፤ የመጀመሪያው ወንጀሉ፤ የረጅም ጊዜ ስቃዩ ፧ ጨካኙ ዓለም፤ የደነደነው ልቡ ፣ ከእስር ቤት ማምለጡ፤ ከጳጳሱ ቤት በእርሱ ላይ የደረሰው! የመጨረሻው አሳፋሪ ድርጊቱ ፤ ከሕፃን ልጅ ገንዘብ መዝረፉ፤
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
.....ከተማውን ጥሎ ወጣ፡፡ ከተማውን ለቅቆ ገጠር እስከገባ ድረስ እየተጣራ ነበር የሚሄደው፡፡ ወዴት እንደሚሄድ ሳያስተውል መንገድ እንደመራው ዝም እያለ ተጓዘ፡፡ ከነጋ ጀምሮ እህል አልቀመሰም:: ሆኖም የረሃብ ስሜት አልተሰማውም፡፡ ቁጣ ቁጣ ብሉታል፡፡ በማን ላይ ወይም በምን ምክንያት እንደተቆጣ ግን አያውቅም:: የሚቀጥለው ምን ይሆን ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡
የገጠር አየር የልጅነት ጊዜውን አስታወሰው:: የልጅነት ዘመኑን ካስታወሰ በጣም ቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም ብዙ ኣሳቦች ተፈራረቁበት፡፡»
ፀሐይ አሽቆልቁላ ገብታ ከአድማስ ውስጥ ልትገባ ስትል ዣን ቫልዣ
እልም ካለ ጫካ ውስጥ ከአንዲት ጉብታ ላይ ቁጭ ብሎአል፡፡ የአልፕስ ተራራ በሩቁ ይታያል፡፡ ከጫካው ወጣ እንዳለ አንድ ቀጭን የእግር መንገድ አለ፡፡
ከዚህ ቁጭ ብሎ ሲያሰላስል ደስ የሚል ድምፅ ይሰማል፡፡ ፊቱን
ሲያዞር ወደ አሥራ ሁለት ዓመት የሚሆነው ልጅ እየዘመረ ወደ እርሱ ይመጣል:: ልጁ በጭንቅላቱ ሣጥን መሳይ ነገር ተሸክሞአል፡፡ ልጁ ጥቂት
ከተራመደ በኋላ ቆም ብሎ በእጁ የያዘውን ሣንቲም ወደ ሰማይ እያጎነ ይጫወታል:: የልጁ ሀብት ምናልባት ይኸው ነጭ ሽልንግ ብቻ ሳይሆን አልቀረም::
ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት ሲደርስ የሰውዬው ከእዚያ መኖር ሳይገነዘብ ቆም አለ፡፡ እንደ ልማዱ ሣንቲሙን ወደ ሰማይ አጎነ፡ ሣንቲሙ አምልጦት
ከመሬት ሊወድቅ ዣን ቫልዣ ወደ ተቀመጠበት በረረ:: ዣን ቫልዣ
ሽልንጉን በእግሩ ረግጦ ያዘበት:: የልጁ ዓይን ሣንቲሙን ተከትሎ ስለሄደ የት ላይ እንዳለ ያውቃል፡፡ ልጁ አልፈራም፤ በቀጥታ ወደ ሰውዬው ሄደ::
«ጌታዬ ገንዘቤን» አለ ልጁ የዋህነትና ድንቁርና በተሞላበት አንደበት::
«ስምህ ማነው?» ሲል ዣን ቫልዣ ጠየቀው::
«ትንሹ ዥራቪ ነው ጌታዬ::»
«ቶሉ ከዚህ ጥፋ» አለው ዣን ቫልዣ ::
«ፍራንኬስ?» ሲል ልጁ ጠየቀ፡፡
ዣን ቫልዣ እንዳቀረቀረ ቀረ::
«ገንዘቤን» አለ ልጁ እምባ እየተናነቀወ :: ሽልንጌን!»
ዣን ቫልዣ ምንም ነገር እንዳልሰማ ሰው ፀጥ አለ፡፡ ልጁ የሰውየውን ሸሚዝ ኮሌታ በአንድ እጁ ያዘ፡፡ በሌላው እጁ ሣንቲሙን ለማስለቀቅ የሰውየውን እግር ለማንሳት ሞከረ::
«ገንዘቤን እፈልጋለሁ ፧ ሽልጌን!» ብሎ ከጮኸ በኋላ ትንሹ ዠራቬ
ማልቀስ ጀመረ:: ዣን ቫልዣ አንገቱን ቀና አደረገ፡፡ ከተቀመጠበት ግን አልተነሳም:: ፊቱ፡ በአሳብ የተዋጠና የተጨነቀ ይመስላል፡፡ በመገረም ልጁን
አትኩሮ አየው:: ዱላውን ሳብ ኣድርጎ «አንተ ማነህ? እህ! ምንድነው የምትፈልገው? እስካሁን አልሄድክም እንዴ» ሲል በሚያስፈራ ድምፅ ጮኸበት:: ሣንቲሙን እንደረገጠ ከመቀመጫው ብድግ ብላ «ራስህን ብትጠብቅ ይሻልሃል» አለው::
ልጁ በፍርሃት ተወጦ ቀና ብላ አየወ:: ሰውነቱ ይንቀጠቀጥ
ጀመር፡፡ ወዲያው ከጥቂት ሰኮንድ መርበትበት በኋላ ልጁ አግሬ አውጪኝ ብሎ ሸመጠጠ፡፡ ዞር ብሎ ለማየት ወይም ጩኸት ለማሰማት እንኳን አልደፈረም፡፡ ሆኖም ጥቂት እንደተጓዘ ትንፋሽ አጥሮት ቆም አለ:: ግን ብዙ
አልቆመም፧ መንገዱን ቀጠለ፡፡
ፀሐይዋ ጠለቀች፡፡ ዣን ቫልዣ ከተቀመጠበት አካባቢ ብርሃን ለጨለማ ሥፍራዋን ለቀቀች:: ቀኑን መሉ ምግብ የሚሉት ነገር አልቀመሰም::ምናልባትም ትንሽ እንደትኩሳት ብጤ ሳይሞካክረው አልቀረም::
ልጁ ከሄደ ጀምሮ ከተቀመጠበት ነቅነቅ አላለም:: በኃይል ነው
የሚተነፍሰው:: ከተቀመጠበት ጥቂት ራቅ ብሎ ከነበረው የሸክላ ስባሪ ገል ላይ ዓይኑን ተከለ፡፡ ስለገሉ ይመራመር ጀመር፡፡ ግን በድንገት መላ ሰውነቱ
ተንቀጠቀጠ፡፡ የሌሊቱ ቁር እየተሰማው ሄደ፡፡
ቆቡን ሳብ አድርጎ ግንባሩን ሸፈነ:: የሸሚዙን አዝራር ለመቆለፍ
ጣቶቹ አዝራር ፍለጋ ላይ ታች አሉ:: ብድግ ብሎ ወደፊት ራመድ ካለ ከኋላ መለስ ብሉ ዱላውን ለማንሳት ጎንበስ አለ፡፡
በእግሩ ረግጦ ይዞት የነበረው ሽልንግ በማብረቅረቁ ዓይኑ ወደዚያ ተሳበ፡፡ ኮረንቲ እንደያዘው ሰው ተሸማቀቀ፡፡ «ምንድነው ነገሩ?» ሲል ጥርሱን በማፋጨት ራሱን ጠየቀ:: እንደገና ወደኋላ መለስ ብሉ ሣንቲሙን በእግሩ በመርገጥ ሸፈነው:: ሣንቲሙ ዓይን አብቅሎ የሚያየው መሰለው::
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ እግሩን መነጨቀና ጎንበስ ብሎ ሣንቲሙን
አነሳ፡፡ ቀና ብሎ አካባቢውን ተመለከተ:: ጋራውና ሸንተረሩ ሁሉ የሚያየው ስለመሰለው በፍርሃት ተውጦ መወጊያ እንደምትፈልግ ዱኮላ ዓይኑ በፍርሃት ተቅበዘበዘ፡፡ ከቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡
ምንም ነገር አላየም:: ጊዜው እየጨለመና አየሩ እጅግ እየቀዘቀዘ ሄደ:: ሰማዩ በጭጋግ ተሸፈነ፡፡
«ወይ ጣጣ» ሲል ልጁ በሄደበት አቅጣጫ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ አንድ
ሰላሳ - እርምጃ ያህል እንደተራመደ ቆም ኣለ፡፡ አካባቢውን ተመለከቱ።
ምንም ነገር የለም:: ድምፁን እጅግ ከፍ አድርጎ «ዠራቬ» ሲል ተጣራ፡፡ ከዚያም ድምፁ
አጥፍቶ አዳመጠ:: መልስ አላገኘም፡፡
አገሩ ጭር ያለና ጭጋጋም ቢሆንም አካባቢው በግልጽ ይታያል ከዝምታና ከራሱ ጥላ በስተቀር የሚንቀሳቀስ ፍጠር ጨርሶ አልነበረም ዣን ቫልዣ መንገዱን ቀጠለ፡፡ የሚወስደውን እርምጃ ፍጥነት በመጨመር እንደ መሮጥ አለ። አልፎ አልፎ ቆም እያለ በሚያስፈራ ሻካራ ድምፅ «ዠራቬ» ሲል እንደገና ተጣራ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ልጁ ቢሰማው
እንኳን በፍርሃት ስለሚዋጥ ይደበቃል እንጂ መልስ አይሰጠውም:: ነገር ግን ልጁ በርግጥም በጣም ርቆ ሄዷል፡፡
ዣን ቫልዣ እንደገና ልጁ በሄደበት ኣቅጣጫ መሮጥ ጀመረ
እየተገላመጠ፣ እየጮኸ፣ እየተጣራ ብዘ ተጓዘ፡፡ ግን ማንንም አላገኘም በደረቱ ተንፏቅቆ የሚሄድ ወይም ድምፁን አጥፍቶ ያደፈጠ እየመሰለ ከአንዴም ሁለቴ፣ ከሁለቴም ሦስቴ መንገዱን ለቅቆ ወደ ጥሻው ዞር እያለ
ተመለከተ፡፡ ግን ሰው የመሰለው ነገር ጠጋ ሲል ቁጥቋጦ ወይም ድንጋ ሆኖ ያገኘዋል፡፡ በመጨረሻ ሦስት መንታ መንገዶች ከሚገናኙበት ደረሰ ከመሐል መንገድ ላይ ቆመ:: ጨረቃዋ ብቅ ብላለች:: ለማየት እስከቻለ
ድረስ አርቆ ተመለከተ:: «ዥራቬ፣ ትንሹ ዥራቬ፣ ዠራቬ» በማለት
ሦስት ጊዜ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተጣራ:: ድምፁ የገደል ማሚቶ እንኳ ሳያዕማ ከጭጋጉ ውስጥ ተውጦ ቀረ:: «ትንሹ ዥራቬ» ሲል ዝግ በደከመ ድምፅ አጉረመረመ:: ያ የመጨረሻው ሙከራ ነበር፡፡ በዓይ የማይታይ ኃይል በዱላ እንደመታው ሰው በድንገት እግሩ ተሳስሮ ጉልበቱ እጥፍጥፍ አለበት:: ፀጉሩን በእጁ ጨብጦና ፊቱን ጉልበቱ ላይ አሳርፎ
ከቋጥኝ ድንጋይ ላይ በመቀመጥ «ምን ዓይነት እድለቢስ ሰው ነኝ» አለ ጮኸ፡፡ ልቡ እያበጠ ሄደ፡፡ ምርር ብሎ አለቀሰ፡፡ ከአሥራ ዘጠኝ ዓመት ወዲህ ሲያለቅስ የመጀመሪያው ነበር:: ዣን ቫልዣ ብዙ አለቀሰ፡፡ ከሕፃኑ መባባትና ከሴቶች መርበትበት ይበልጥ በፍርሃት ተውጦ ከዓይኑ እምባ የወጣ እስኪመስለው ድረስ በማልቀስ አንጀቱን እርር ድብን አደረገ እያለቀሰ ሳለ ከሕሊናው ውስጥ የነበረው ብርሃን እየፈካ ሄደ፡፡
የተለየ ብርሃን ነበር፡፡ ያ ብርሃን አሳደደው፤ አስፈራራው፡፡ ያለፈው የሕይወቱ ዘመን፤ የመጀመሪያው ወንጀሉ፤ የረጅም ጊዜ ስቃዩ ፧ ጨካኙ ዓለም፤ የደነደነው ልቡ ፣ ከእስር ቤት ማምለጡ፤ ከጳጳሱ ቤት በእርሱ ላይ የደረሰው! የመጨረሻው አሳፋሪ ድርጊቱ ፤ ከሕፃን ልጅ ገንዘብ መዝረፉ፤
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
.....“ያንቺ ነዉ” አለችኝ፣ እኛ እያለን ራሷ ወደ ጀመረችዉ የምሳ ጉድ ጉዷ እየተመለሰች፡፡ “ታዲያ አደራሽን ምንድነዉ ቅብጥርሴ እንዳትጠኝ። እኔ ምኑንም አላዉቅልሽም። ስጭ ነበር የተባልሁት፣ ይኼዉ ሰጥቼሻለሁ።
አበቃሁ” በእራፊ ጨርቅ የተጠቀለለች ትንሽ ነገር መሆኗን ቀድሞዉንም ስትሰጠኝ
ኣስተዉያለሁ፡፡ ምን እንደሆነች ለማየት ገለጥ ባደርጋትም፣ ጥቅልሉ ስለበዛ ፍሬ እቃዋን ቶሎ ልደርስበት አልቻልሁም፡፡ ስቀበላት እምነት መስላኝ ነበር። አይደለችም ማለት ነዉ? በዚያ ላይ ስንት ዙር እንደ
ተጠቀለለች! ተርትሬ ተርትሬ ስጨርስ ያገኘሁት ግን ጥፍር እንኳን የማታህል ሚሞሪ ካርድ ብቻ ነበረች፡፡ መጠቅለያ ጨርቁን ባራግፈዉም፣ ከእሷ ሌላ ምንም የለም። እመዋ ደግሞ እንዳልጠይቃት ቀድማ መንገዱን
ሁሉ ዘጋግታብኛለች፡፡ ምን ቸገረኝ ብዬ ወደ ሞባይሌ ቀፎ ከተትኋት።
ከዚያም በድምፅ ማጫወቻዉ ከፈትሁት፡፡ ከትንሽ የነፋስ እና የወፎች ጺዉጺዉታ በኋላ፤ ማሲንቆ የሚያስንቅ አንቺሆዬ ዓይነት ፉጨት መጣ፡፡
የት ነበር የማዉቀዉ ይኼን ድንቅ ትንፋሽ?
መቼ አጣኋቸዉ! ወይዘሮ ብርሃኔ ናቸዉ፡፡ እሳቸዉ ናቸዉ ትንፋሻቸዉን እንደ ፈለጉ የሚያሽሞነሙኑት። እንኳን በሴት በወንድ እንኳን የማላዉቀዉን፣ ማንኛዉንም ዜማ በፉጨታቸዉ ብቻ ሲያወጡት አያድርስ ነዉ። በዘለሰኛ ጨዋታቸዉ የሁሉን ነፍስ የሚገዙት፣ በሸክላ ሥራ ጥበባቸዉ ሁሉን የሚያስደንቁት፣ ፉጨት እና ሽለላዉን
የሚያዉቁበት፣ ወይዘሮ ብርሃኔ ናቸዉ። አትጠገቤዋ፣ ደርባባዋ ሰዉ! በእርግጥ መጀመሪያ ያወቅኋቸዉ በእሸቴ በኩል ነበር። የእሱ እናት ናቸዉ፡፡ እንደ ጣና ሐይቅ የተረጋጉት፣ እንደ ዥማ ወንዝ የልብ የሚያደርሱት ሴት ናቸዉ በፉጨት የመጡብኝ። ጥሎብኝ አንጎራጓሪ ሰዉ
አይሆንልኝም፡፡ እጅግ አድርጌ እወዳለሁ። በተለይ ዘለሰኛ! ዘለሰኛ ለመስማት ስል ምንም ነገር ቢሆን እተዋለሁ። አሁን አሁን እንዲህ እሸቴ የሚባል ስም በአፍንጫዬ ይውጣ ልል፣ ያኔ ልቤን ወለል አድርጌ
እንድከፍትለት ካደረገበት ብዙ ምክንያቶቹ አንዷ እናቱ ነበሩ።
ልዩ ናቸዋ!
ፉጨቱን ተከትሎ በድምፃቸዉ ደግሞ መጡብኝ። ያ ከእሕልም
ከመጠጥም የሚጣፍጠዉ ዘለሰኛቸዉ!
ኧኧኧኧኧኧ...
ሸክላ ሠሪ አርገህ ሾመኸኛል
የሸክላ ጥበብ ይገባኛል፡፡
ኧኸ
ሸክላ ማለት የእጄ ሥራ
እኔ ደግሞ የእጅህ ሥራ፤
የእጄ ተሰብሮ ብመኝም ሞት
የእጅህን ማትረፍ ግን አወቅህበት!
ኧ ኸ ኧ ኸ ኧ.....
ምንም እንኳን ቀረጻዉ ጥራት ያልሞላለት ሆኖ ሞገዱ እንደሚዋዥቅበት ሬዲዮ ወስድ መለስ ሲያደርገዉም፣ እየደጋገምሁ አጣጣምሁት። ከምኔዉ እንደሆነ እንጃልኝ ብቻ አሁን መረጋጋት ይታይብኛል። አሁን ከፋኝ ብዬ ስነፈርቅ አልነበር እንዴ? ፊቴን ዳበስሁት፤ እንባ የሚባል ጠብታዉ ሳይቀር የለም። ወደ መስታዎት ሮጬ ዓይኔን አየሁት። እንኳንስ ደም
ሊመስል! ልክ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ወደ ነባሩ ቀልቤ ተመልሻለሁ። ያውም ወደ ደስተኛዋ ዉብርስት። ጃሪም የለ፣ እሸቴ የለ፣ እርግዝና የለ
ሁሉም ደህና። ፍጹም ሰላም፡፡
“እመዋ?” አልኋት፣ እንጀራ ይዛ ወደ ሳሎን ብቅ ከማለቷ፡፡
ለወጉ ያህል ብቻ ቀና ብላልኝ፣ ወደ ማዕድ ቤት አልፋኝ ሄደች። ምን ላርግሽ፣ ይልቅ ማቀራረቡን አትረጅኝም? ማለቷ መሰለኝ። ከምኔዉ እንዲህ እንደ ተረጋጋሁ እሷንም ሳይደንቃት አልቀረም።
“ማነዉ የሰጠሽ ግን?” አልኋት፣
እግር በእግር እየተከታተልኳት።
“ማን ይመስልሻል?” አለችኝ፣ ፍርጥም ብላ።
“ብቻ እሽቴ ነዉ እንዳትዪኝ በማርያም”
“እሸቴ የሆነ እንደሆንስ? ስጦታ ሁሉ ያዉ ስጦታ አይደለም ወይ?”
“እህእ?”
ስጦታ ሁሉማ ያዉ አይደለም፡፡ ከእሸቴ ነዉ ማለት ነዉ? እንደ ፈራሁት መልሶ ከፋኝ፡፡ እንደገና ስምጥ ወደ ሆነዉ ድባቴ ዉስጥ ተወርዉሬ ወደቅሁ። መቼም ከእሱ ሌላ የእናቱን ድምፅ ቀርጾ በእናቴ በኩል የሚልክልኝ አይኖርም፡፡ ለዚያዉም ድምፁ ሌሊት ወፍ ጭጭ ሲል በድብቅ የተቀረጸ ነዉ የሚመስለዉ። ስለዚህ አብሮ የሚያድር ሰዉ ነዉ ማለት ነዉ የቀረጻቸዉ፡፡ ያም ሰዉ ከእሸቴ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ እሱ
ነዉ የላከልኝ። እጅ መንሻ መሆኑ ነዉ? የተጣላነዉ በእናቱ ይመስል፣ በዚህ ሊያባብለኝ መሞከሩ የበለጠ እልህ ዉስጥ ጨመረኝ፡፡
እናቱ ሌላ፣ እሱ ሌላ።
ራሴን ግን ታዘብሁት፡፡ ቶሎ የሚከፋኝ፣ ቶሎ የምደሰት ግልብ ሆኜ አርፌዋለሁ ማለት ነዉ በቃ? አሁን ለቅሶ፣ አሁን ሳቅ፣ እንደገና ለቅሶ?
ሰአሊ ለነ ቅድስት!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሐዘንም ሐፍረትም ቀላቅሎ ከመታኝ ይኸዉ ቀናት አለፉ፡፡ ያዉም እንደ ሙጀሌያም እየተሙጀለጀሉብኝ። በእነዚህ ቀናት ሁሉ በእመዋ ቤት ተደብቼ ራሴን አዳመጥሁት። እንደ ወትሮዬ ወደ አደባባይ ሳልወጣ፣
እንደ ድሮዉ በወዳጅ ሳልከበብ፣ እንደ ሁልጊዜዉ ወደ ሲራክ-፯ ማዕከል ሳልመላለስ ዐሥራ አንድ ረዣዥም ቀናት እያለፉኝ ሄደዋል። እንዲሁ አልፎ አልፎ ብቻ ሲልብኝ፣ ክራሬን አንስቼ ለብቻዬ እያንጎራጎርሁ በእናቴ ቤት ሰነበትሁ፡፡
በዚህ ምክንያት እመዋም ሁኔታዬን እያየች ስትብሰለሰል፣ እያሳዘነችኝ መጣች፡፡ ምናልባት ዘወር ብልላት ይቀላት እንደሆነ ብዬ፣ ሲራክ-፯ ለአንዳንድ ተልእኮዎች በማሰብ በምስጢር ቀድሞም ወደ ተከራየልኝ
ምስጢራዊዋ ቤት ደግሞ ሄድሁ። ይቺ ቤት፣ በተልእኮዬ ሂደት መሀል
እንድቀራረባቸዉ የሚያስገድዱ ሰዎች ቢኖሩ ቤቴ ብዬ የማሳያቸዉ ቤት ናት። እንደ ሁኔታዉ፣ እነዚህ ዒላማ የተደረጉ ሰዎች ረዥም ጊዜ እና የተለየ መቀራረብ የግድ የሚፈልጉ ስለሚሆን፣ የቤት ቡና የምጋብዛቸዉ በእመዋ ቤት ባለኝ ክፍል ሳይሆን፣ በዚሁ ምስጢራዊ የኪራይ ቤት ነዉ።
ወደ'ዚህ ቤት እንደመጣሁ፣ እመዋ አዘዉትራ እሸቴ ምን በደለሽ?»
ስትለኝ የሰነበተችዉ ጥያቂ ድንገት ሽዉ አለችብኝ፡፡ ገና ዛሬ፣ አሁን ገና። እንደገና አስብሁበት:: እዉነትስ ግን እሱ ምን በድሎኛል? ምንም። ምንም ወንጀል አጣሁበት። ቆይ እኔ ራሴ አይደለሁ እንዴ፣ ዓለም በቃኝ ብሎ
ከመነነበት የእናቱ ከተማ ሄጄ የተዋወቅሁት? እኔ ባልሄድበት እንኳንስ መበደል፣ ጭራሽ የት ያዉቀኝ ኖሯል? ደረስሁበት እንጂ አልደረሰብኝም እኮ፡፡ ይልቅስ ራሴ ነኝ በገዛ ሕይወቴ የተጫወትሁት። እኔን ማንም አልበደለኝም። ከተበደልሁም የተበደልሁት በራሴ ነዉ። እኔዉ ነኝ ራሴንም እግዚአብሔርንም የበደልሁት። ስለዚህ ራሴን ለካህን ማሳየት
አለብኝ።
ንስሐ ያስፈልገኛል።
ወዲያዉኑ ተስፈንጥሬ ተነሳሁና፣ ነጠላዬን እንደ ነገሩ አንገቴ ላይ ጥዬ ወደ መኪናዬ ሮጥሁ። ምስጢራዊዋ ቤቴ በአዲስ አበባ ልዩ ሰፈሩ ልደታ በሚባለዉ የምትገኝ ኮንዶሚኒየም ስለሆነች፣ ተዘግቶ እስከሚከፈት
የሚያጉላላኝ የአጥር በር የለብኝም፡፡ ይቺን መከራ ቻይ መኪናዬን ዛሬም ያለቅጥ ረግጬ አበረርኋት። የትራፊክ መብራት የሚባል ለቅጽበት አላስቆመኝም። ንስሐ አባቴ የሚያገለግሉት እዚሁ ልደታ ጎን ባለዉ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቢሆንም፣ በዚህ አመሻሽ ግን እሳቸዉ የት
እንዳሉ አላዉቅም። በቤታቸዉ ሊሆኑ እንደሚችሉ በመገመት ነበር ቀጥታ ወደ መኖሪያ ቤታቸዉ የሄድሁ። እዚያ ስደርስ ግን አጣኋቸዉ።
አቤት ጥድፊያ! ስልክ ቁጥራቸዉ አለኝ አይደል እንዴ?
ደወልሁላቸዉ።
“እዚያዉ ልደታ እኮ ጉባዔ ላይ ነበርሁ። ምናለ ከመድከምሽ ፊት ደዉለሽ ብትጠይቂኝ ኖሮ ልጄ?” አሉኝ፣ በሐዘኔታ፡፡
“ግድየለም፡፡ እዚያዉ ልምጣ ታዲያ?”
“ምን ገዶኝ? ነይ በይ እዚሁ”
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
.....“ያንቺ ነዉ” አለችኝ፣ እኛ እያለን ራሷ ወደ ጀመረችዉ የምሳ ጉድ ጉዷ እየተመለሰች፡፡ “ታዲያ አደራሽን ምንድነዉ ቅብጥርሴ እንዳትጠኝ። እኔ ምኑንም አላዉቅልሽም። ስጭ ነበር የተባልሁት፣ ይኼዉ ሰጥቼሻለሁ።
አበቃሁ” በእራፊ ጨርቅ የተጠቀለለች ትንሽ ነገር መሆኗን ቀድሞዉንም ስትሰጠኝ
ኣስተዉያለሁ፡፡ ምን እንደሆነች ለማየት ገለጥ ባደርጋትም፣ ጥቅልሉ ስለበዛ ፍሬ እቃዋን ቶሎ ልደርስበት አልቻልሁም፡፡ ስቀበላት እምነት መስላኝ ነበር። አይደለችም ማለት ነዉ? በዚያ ላይ ስንት ዙር እንደ
ተጠቀለለች! ተርትሬ ተርትሬ ስጨርስ ያገኘሁት ግን ጥፍር እንኳን የማታህል ሚሞሪ ካርድ ብቻ ነበረች፡፡ መጠቅለያ ጨርቁን ባራግፈዉም፣ ከእሷ ሌላ ምንም የለም። እመዋ ደግሞ እንዳልጠይቃት ቀድማ መንገዱን
ሁሉ ዘጋግታብኛለች፡፡ ምን ቸገረኝ ብዬ ወደ ሞባይሌ ቀፎ ከተትኋት።
ከዚያም በድምፅ ማጫወቻዉ ከፈትሁት፡፡ ከትንሽ የነፋስ እና የወፎች ጺዉጺዉታ በኋላ፤ ማሲንቆ የሚያስንቅ አንቺሆዬ ዓይነት ፉጨት መጣ፡፡
የት ነበር የማዉቀዉ ይኼን ድንቅ ትንፋሽ?
መቼ አጣኋቸዉ! ወይዘሮ ብርሃኔ ናቸዉ፡፡ እሳቸዉ ናቸዉ ትንፋሻቸዉን እንደ ፈለጉ የሚያሽሞነሙኑት። እንኳን በሴት በወንድ እንኳን የማላዉቀዉን፣ ማንኛዉንም ዜማ በፉጨታቸዉ ብቻ ሲያወጡት አያድርስ ነዉ። በዘለሰኛ ጨዋታቸዉ የሁሉን ነፍስ የሚገዙት፣ በሸክላ ሥራ ጥበባቸዉ ሁሉን የሚያስደንቁት፣ ፉጨት እና ሽለላዉን
የሚያዉቁበት፣ ወይዘሮ ብርሃኔ ናቸዉ። አትጠገቤዋ፣ ደርባባዋ ሰዉ! በእርግጥ መጀመሪያ ያወቅኋቸዉ በእሸቴ በኩል ነበር። የእሱ እናት ናቸዉ፡፡ እንደ ጣና ሐይቅ የተረጋጉት፣ እንደ ዥማ ወንዝ የልብ የሚያደርሱት ሴት ናቸዉ በፉጨት የመጡብኝ። ጥሎብኝ አንጎራጓሪ ሰዉ
አይሆንልኝም፡፡ እጅግ አድርጌ እወዳለሁ። በተለይ ዘለሰኛ! ዘለሰኛ ለመስማት ስል ምንም ነገር ቢሆን እተዋለሁ። አሁን አሁን እንዲህ እሸቴ የሚባል ስም በአፍንጫዬ ይውጣ ልል፣ ያኔ ልቤን ወለል አድርጌ
እንድከፍትለት ካደረገበት ብዙ ምክንያቶቹ አንዷ እናቱ ነበሩ።
ልዩ ናቸዋ!
ፉጨቱን ተከትሎ በድምፃቸዉ ደግሞ መጡብኝ። ያ ከእሕልም
ከመጠጥም የሚጣፍጠዉ ዘለሰኛቸዉ!
ኧኧኧኧኧኧ...
ሸክላ ሠሪ አርገህ ሾመኸኛል
የሸክላ ጥበብ ይገባኛል፡፡
ኧኸ
ሸክላ ማለት የእጄ ሥራ
እኔ ደግሞ የእጅህ ሥራ፤
የእጄ ተሰብሮ ብመኝም ሞት
የእጅህን ማትረፍ ግን አወቅህበት!
ኧ ኸ ኧ ኸ ኧ.....
ምንም እንኳን ቀረጻዉ ጥራት ያልሞላለት ሆኖ ሞገዱ እንደሚዋዥቅበት ሬዲዮ ወስድ መለስ ሲያደርገዉም፣ እየደጋገምሁ አጣጣምሁት። ከምኔዉ እንደሆነ እንጃልኝ ብቻ አሁን መረጋጋት ይታይብኛል። አሁን ከፋኝ ብዬ ስነፈርቅ አልነበር እንዴ? ፊቴን ዳበስሁት፤ እንባ የሚባል ጠብታዉ ሳይቀር የለም። ወደ መስታዎት ሮጬ ዓይኔን አየሁት። እንኳንስ ደም
ሊመስል! ልክ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ወደ ነባሩ ቀልቤ ተመልሻለሁ። ያውም ወደ ደስተኛዋ ዉብርስት። ጃሪም የለ፣ እሸቴ የለ፣ እርግዝና የለ
ሁሉም ደህና። ፍጹም ሰላም፡፡
“እመዋ?” አልኋት፣ እንጀራ ይዛ ወደ ሳሎን ብቅ ከማለቷ፡፡
ለወጉ ያህል ብቻ ቀና ብላልኝ፣ ወደ ማዕድ ቤት አልፋኝ ሄደች። ምን ላርግሽ፣ ይልቅ ማቀራረቡን አትረጅኝም? ማለቷ መሰለኝ። ከምኔዉ እንዲህ እንደ ተረጋጋሁ እሷንም ሳይደንቃት አልቀረም።
“ማነዉ የሰጠሽ ግን?” አልኋት፣
እግር በእግር እየተከታተልኳት።
“ማን ይመስልሻል?” አለችኝ፣ ፍርጥም ብላ።
“ብቻ እሽቴ ነዉ እንዳትዪኝ በማርያም”
“እሸቴ የሆነ እንደሆንስ? ስጦታ ሁሉ ያዉ ስጦታ አይደለም ወይ?”
“እህእ?”
ስጦታ ሁሉማ ያዉ አይደለም፡፡ ከእሸቴ ነዉ ማለት ነዉ? እንደ ፈራሁት መልሶ ከፋኝ፡፡ እንደገና ስምጥ ወደ ሆነዉ ድባቴ ዉስጥ ተወርዉሬ ወደቅሁ። መቼም ከእሱ ሌላ የእናቱን ድምፅ ቀርጾ በእናቴ በኩል የሚልክልኝ አይኖርም፡፡ ለዚያዉም ድምፁ ሌሊት ወፍ ጭጭ ሲል በድብቅ የተቀረጸ ነዉ የሚመስለዉ። ስለዚህ አብሮ የሚያድር ሰዉ ነዉ ማለት ነዉ የቀረጻቸዉ፡፡ ያም ሰዉ ከእሸቴ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ እሱ
ነዉ የላከልኝ። እጅ መንሻ መሆኑ ነዉ? የተጣላነዉ በእናቱ ይመስል፣ በዚህ ሊያባብለኝ መሞከሩ የበለጠ እልህ ዉስጥ ጨመረኝ፡፡
እናቱ ሌላ፣ እሱ ሌላ።
ራሴን ግን ታዘብሁት፡፡ ቶሎ የሚከፋኝ፣ ቶሎ የምደሰት ግልብ ሆኜ አርፌዋለሁ ማለት ነዉ በቃ? አሁን ለቅሶ፣ አሁን ሳቅ፣ እንደገና ለቅሶ?
ሰአሊ ለነ ቅድስት!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሐዘንም ሐፍረትም ቀላቅሎ ከመታኝ ይኸዉ ቀናት አለፉ፡፡ ያዉም እንደ ሙጀሌያም እየተሙጀለጀሉብኝ። በእነዚህ ቀናት ሁሉ በእመዋ ቤት ተደብቼ ራሴን አዳመጥሁት። እንደ ወትሮዬ ወደ አደባባይ ሳልወጣ፣
እንደ ድሮዉ በወዳጅ ሳልከበብ፣ እንደ ሁልጊዜዉ ወደ ሲራክ-፯ ማዕከል ሳልመላለስ ዐሥራ አንድ ረዣዥም ቀናት እያለፉኝ ሄደዋል። እንዲሁ አልፎ አልፎ ብቻ ሲልብኝ፣ ክራሬን አንስቼ ለብቻዬ እያንጎራጎርሁ በእናቴ ቤት ሰነበትሁ፡፡
በዚህ ምክንያት እመዋም ሁኔታዬን እያየች ስትብሰለሰል፣ እያሳዘነችኝ መጣች፡፡ ምናልባት ዘወር ብልላት ይቀላት እንደሆነ ብዬ፣ ሲራክ-፯ ለአንዳንድ ተልእኮዎች በማሰብ በምስጢር ቀድሞም ወደ ተከራየልኝ
ምስጢራዊዋ ቤት ደግሞ ሄድሁ። ይቺ ቤት፣ በተልእኮዬ ሂደት መሀል
እንድቀራረባቸዉ የሚያስገድዱ ሰዎች ቢኖሩ ቤቴ ብዬ የማሳያቸዉ ቤት ናት። እንደ ሁኔታዉ፣ እነዚህ ዒላማ የተደረጉ ሰዎች ረዥም ጊዜ እና የተለየ መቀራረብ የግድ የሚፈልጉ ስለሚሆን፣ የቤት ቡና የምጋብዛቸዉ በእመዋ ቤት ባለኝ ክፍል ሳይሆን፣ በዚሁ ምስጢራዊ የኪራይ ቤት ነዉ።
ወደ'ዚህ ቤት እንደመጣሁ፣ እመዋ አዘዉትራ እሸቴ ምን በደለሽ?»
ስትለኝ የሰነበተችዉ ጥያቂ ድንገት ሽዉ አለችብኝ፡፡ ገና ዛሬ፣ አሁን ገና። እንደገና አስብሁበት:: እዉነትስ ግን እሱ ምን በድሎኛል? ምንም። ምንም ወንጀል አጣሁበት። ቆይ እኔ ራሴ አይደለሁ እንዴ፣ ዓለም በቃኝ ብሎ
ከመነነበት የእናቱ ከተማ ሄጄ የተዋወቅሁት? እኔ ባልሄድበት እንኳንስ መበደል፣ ጭራሽ የት ያዉቀኝ ኖሯል? ደረስሁበት እንጂ አልደረሰብኝም እኮ፡፡ ይልቅስ ራሴ ነኝ በገዛ ሕይወቴ የተጫወትሁት። እኔን ማንም አልበደለኝም። ከተበደልሁም የተበደልሁት በራሴ ነዉ። እኔዉ ነኝ ራሴንም እግዚአብሔርንም የበደልሁት። ስለዚህ ራሴን ለካህን ማሳየት
አለብኝ።
ንስሐ ያስፈልገኛል።
ወዲያዉኑ ተስፈንጥሬ ተነሳሁና፣ ነጠላዬን እንደ ነገሩ አንገቴ ላይ ጥዬ ወደ መኪናዬ ሮጥሁ። ምስጢራዊዋ ቤቴ በአዲስ አበባ ልዩ ሰፈሩ ልደታ በሚባለዉ የምትገኝ ኮንዶሚኒየም ስለሆነች፣ ተዘግቶ እስከሚከፈት
የሚያጉላላኝ የአጥር በር የለብኝም፡፡ ይቺን መከራ ቻይ መኪናዬን ዛሬም ያለቅጥ ረግጬ አበረርኋት። የትራፊክ መብራት የሚባል ለቅጽበት አላስቆመኝም። ንስሐ አባቴ የሚያገለግሉት እዚሁ ልደታ ጎን ባለዉ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቢሆንም፣ በዚህ አመሻሽ ግን እሳቸዉ የት
እንዳሉ አላዉቅም። በቤታቸዉ ሊሆኑ እንደሚችሉ በመገመት ነበር ቀጥታ ወደ መኖሪያ ቤታቸዉ የሄድሁ። እዚያ ስደርስ ግን አጣኋቸዉ።
አቤት ጥድፊያ! ስልክ ቁጥራቸዉ አለኝ አይደል እንዴ?
ደወልሁላቸዉ።
“እዚያዉ ልደታ እኮ ጉባዔ ላይ ነበርሁ። ምናለ ከመድከምሽ ፊት ደዉለሽ ብትጠይቂኝ ኖሮ ልጄ?” አሉኝ፣ በሐዘኔታ፡፡
“ግድየለም፡፡ እዚያዉ ልምጣ ታዲያ?”
“ምን ገዶኝ? ነይ በይ እዚሁ”
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...አሮጌዉ ቤት በጨረቃ ብርሃን ሲታይ ጸጥ ቅዝቅዝ ብሎ ነበር " ያንለት ደግሞ ጨረቃዋ በጣም ደምቃለች « በብርሃንዋ ሰፊው ያታክልት ቦታም ዳር እስከ ዳር
ቁልጭ ብሎ ይታያል " በአየር ሁኔታ ማሳያው ያውራ ዶሮ ምሥል በበረንዳውና በባርባራ ላይም በማብራቷ ተለይተው ይታወቃሉ ባርባራ በረንዳውን ቀስ ብላ
አልፋ በፍርሃት ለጭንቀት እንዳፈጠጠች ከአትክልቱ ሥፍራ በታች ወደነበሩት እጅብ ያሉት ዛፎች ወረደች ያ ከዱሩ ወጥቶ እሷን በድብቅ ሲጠቅሳት የነበረው
ፍጡር ሌላ ተጨማሪ መዘዝ ይዞ የመጣ ሰው ይሆን ? ወይም †ፈጥሮው ከሰው የተለየ ልዩ ጉድ ነው ? ወይስ በውን የሌለ በሐሳብ ብቻ የተፈጠረ ባዶ ራዕይ ነው?
የሚሉ ጥያቄዎች በባርባራ አእምሮ ሲተራመሱባት አሁንም ቀረብ ብሎ ጠቀሳት ባርባራ ከፍራቷ የተነሣ እግሮቿ እየተንቀጠቀጡ ያንገት ልብሷን ጭምድድ አድርጋ ያዘች በጠራው ጨረቃ እሷ ወደሱ ስትጠጋ እሱ ደግሞ ወደ ዛፎቹ ጥላ አፈገፈገ" ባርባራ ቆም አለች
« ማነህ ? ምንድነህ ? » አለችው ድምጿን ዝቅ አድርጋ!«ምን ትፈልጋለህ ? »
« ባርባራ » ብሎ ጠራት በሹክሹክታ ድምፅ «አላወቅሽኝም ? » ገና ከመናገሩ
ድምፁ በትክክል ለየችው » ከደስታ ይልቅ ፍራት ያመዘነበት ድምፅ አሰምታ ተንደርድራ ወደሱ ሔዶች » በእርሻ ሥራ የዋለ ገበሬ የሚለብሰውን ዐይነት ልብስ
የለበሰ ሰው በክንዶቹ ዕቅፍ ሲያደርጋት ሥቅሥቅ ብላ አለቀሰች " የሥራ ካፖርት
ደርቦ የሣር ባርኔጣ ደፍቶ ሰው ሠራሽ ሪዝ አድርጎ ፍጹም ሌላ ሰው መስሎ ቢመጣም ወንድሟ መሆኑን ዐወቀችው
« ሪቻርድ ! ከየት መጣህ ? ከዚህ ምን አመጣህ ? እኔ ደግሞ ምናልባት ካንተ የተላከ ሰው እንደሆነ ብዬ ተጠራጠርኰ እንጂ እንደዚህ ሆነህ ትመጣለህ ብዬ
አላሰብኩም " አሁንም በጣም ነው ያስደነገጥኸኝ እውነት በጤናህ ነው ወይስ ዐብደህ የመጣኸው ? እዚህ ብትገኝ ሞት እንደሚጠብቅህ እያወቅህ እንዴት ደፍረሀ ትመጣለህ ? » አለችው እጆቿን እያፋተገች
«ያውም ከወንጀለኛ መስቀያ ላይ ነዋ እንደምገደል መች ጠፋኝ ባርባራ ዐውቀዋለሁ " »
« ታዲያ ለምንድን ነው ወደ መጥፈያህ ስተት ብለህ የመጣህ ? እማማ ብታይህ
በአድራጐትህና በድፍረትህ ደንግጣ ትሞታለች »
« ኑሮውን አልቻልኩትም ከወጣሁ ጀምሮ እስከ ዛሬ ለንደን ስሠራ ነበር ነገር ግን በዚሁ ዐይነት መግፋት አልቻልኩም
" ትንሽ ገንዘብ ባገኝ ግን ከዚህ የተሻለ ዕድል አለኝ " ስለዚህ አማማ ጥቂት ገንዘብ ብትሰጠኝ ለመጠየቅ ነው የመጣሁት»
« እስከ ዛፊ ምን ትሠራ ነበር ? »
« በአንድ የፈረሶች ጋጣ ውስጥ ነበር የምሠራው " »
« ምን ! በፈረሶች ጋጣ ? »
አለችው የእውነቷን ድንግጥ ብላ»
"ከዚህ የተሻለ ምን ዕድል ሊኖረኝ ይችላል ? ነጋዴ ? ባንከኛ ? መይስ የንድ ሚኒስትር ልዩ ጸሐፊ መሆን ? ነው ወይስ ንብረት ኖሮኝ በሀብቴ ልተዳደር?» አላት
የሆዱ ብሶት እየተናነቀው « አየሽ የምተዳደረው በሳምንት በማገኛት
ዐሥራ ሁለት ሽልንግ ብቻ ነው»
« አዬ ሪቻርድ ! » አለች እጁን ግጥም አድርጋ ይዛ እያለቀስች
« እንዴት ያሉ ጐደሎ ቀን ነው ? አየህ ......... እኛ የምንጽናናው ድርጊቱ በደም ፍላት እንጂ
ሆን ብለህ እንዳልፈጸምከው በማሰብ ብቻ ነው»
« ባርባራ እኔ እኮ ምንም ወንጀል አልፈጸምኩም »
« ምን? »
« በውነት እምልልሻለሁ ። ከደሙ ንጹሕ ነኝ እንዳያውም ሰውየው ሲገደል እኔ ከቦታወ አልነበርኩም " እስከማውቀው ድረስ በግምት ካልሆነ በቀር እገሌ ሲገድል አየሁ ብዬ በዐይን ምስክርነት መናገር እንኳ አልችልም " አላየሁም "
ግምቴ ግን ከማየት የማያንስ ትክክለኛ ነው »
ባርባራ አሁን በበላጠ አንዘረዘራት « መቸም ወንጀሉን የፈጸው ቤተል
ማለትህ እንዳልሆነ እርግኛ ነኝ »
« ቤተል ? እሱም በነገሩ የለበትም እሱ ለራሱ በድብቅ አውሬ ያድን
ነበር ፤ ወጥመዶቹን ነበር የሚከታተል »
« እማማ ግን በወንጀሉ የቤተል እጅ አለበት ያለች አላስቀምጠኝ አለች»
« ተሳስታለች እሱን እንድትጠረጥር ያዪረጋት ምንድነው ? »
« ከመጀመሪያ ይህ እምነት እንዴት እንዳደረባት ልነግርህ አልችልም እሷም ራሷ የምታውቀው አይመስለኝም " ወትሮም ቢሆን ምን ያህል ደካማ እንዶሆነችና በሐሳቧ የሚመጣባትን ሁሉ እውነት መስሎ እንደሚታያት አንተም ታስታውሳለህ አሁን ከዚያ አሠቃቂ ምሽት ጀምሮ ስለ ግድያው ሁልጊዜ ሕልም ታየኝ ትላለች በሕልሟ ውስጥ ሁሉ ቤተልም አብሮ ይታያታል " ስለዚህ ቤተል በነገሩ እንዳለበት ያለ ምንም መጠራጠር ታምናለች »
« ባርባራ እሱ በዚህ ጉዳይ አልነበረበትም »
« አንተ እንዳልነበርክበት ነው አሁን የምትነግረኝ ? »
« እኔ በዚያን ጊዜ ከሆሊጆን ቤትም አልነበርኩ " ወንጀሉን የፈጸመ ቶርን ነው»
« ቶርን ? » አለች አንገቷን ቀና አድርጋ « ቶርን ማነው ? »
« እንጃ ! ባውቀው ደስ ይለኝ ነበር ከገባበት መዝዤ ባወጣው በወደድኩ ሰውየው የአፊ ወዳጅ ነበር ። »
“ሪቻርድ !! ... ይህን ስም ስታነሣብኝ ራስህን የዘነጋህ መስልከኝ ” አልችው አንገቷን በቁጣ ወዶ ኋላ ምልስ አድርጋ
«እኔ!ኮ አንድ ጊዜ ያበላሸሁት ስለሆነ በጉዳዩ ለመነጋገር አልሻም " አሁን ስለ ንጽሕናዬ ብናገር ሪቻርድ ሔር ትንሹ በፈጸመው የግፍ ግድያ ተብሎ የተላለፈብኝን ውሳኔ ሊያስለውጥልኝ አይችልም። ግን አባባ ዛሬም እንደ ጠላኝ ነው »
«ከፊቱ ስምህን የሚያነሣ የለም " ከቤት አንድም ሰው ስምህን እንዳይጠራ ለአሽከርቹ በሙሉ ትእዛዝ ሰጥቶአል " ያቺ ኤልሳ መቸም የተነገረችውን ማስታወስ አይሆንላትም " መኝታ ቤትህን የሚስተር ሪቻርድ ክፍል " እያለች ስትናገር ሁለት ጊዜ ቢያስጠነቅቃትም እየረሳች መተው አልቻለችም " በሦስተኛው ከቤት አባረራት ። አባባኮ ምሏል ሰም†ሃል ? »
« ምን ብሎ ? እሱ ሁልጊዜ እንደማለ ነው »
« ያሁኑ ግን ከባድ መሐላ ነው ሪቻርድ።ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ከ0ሥር ዓመት በኋላ ቢገኝ እንኳን አሳልፎ እንደሚሰጥህ ከዳኞቹ ፊት ቁሞ በመማል አረጋግጦላቸዋል እሱ አንድ ጊዜ ከተናገረ እንደማይመለስ ታውቀዋለህ » ስለዚህ ያንተ ከዚህ አካባቢ መገኘት አደገኛ ነው»
« እሱኮ ዱሮውንም እንዶ ልጁ እንዳልቆጠረኝ ሊያደርግልኝ የሚገባውን እንዳላደረገልኝ ዐውቃለሁ » አለ ምርር ባለ አነጋገር « እስኪ አንቺ ስታስቢው
ጤና በማጣቴ ምስኪኗ እናቴ ስለ ተንከባከበችኝ በየደረሰበት ላገኘው ሰው ሁሉ ተሞላቀቀ እያለ ሊያሥቅብኝ ይጥር ነበር እኔ ቢቴ የደስታ ቤት ቢሆንልኝ ኖሮ ይኸ ሁሉ መቸ ይደርስብኝ ነበር ? በይ አሁን ... ...ባርባራ እናቴ ጋር ዐይን ለዐይን ተያይተን መነጋገር አለብን»
ባርባራ ከመናገሯ በፊት ትንሽ አሰበች« እንዴት እንደ ምናሳካው አላውቅም»
« ለምን አንቺ እንደ መጣሺው እሷስ ወደኔ አትመጣም? ለመሆኑ ተኝታለች ወይስ ተነሥታለች ? »
« ዛሬ ከሷ ጋር መተያየት የማይሆን ነገር ነው አባባ ሳናስበው ሊመጣ ይችላል
አሁን ያለው ከቦሻ ቤት ነው»
« ዐሥራ ስምንት ወር ሙሉ ሳንተያይ ኖረን አሁን ደግሞ ሳላገኛት ብሔድ በጣም ከባድ ነገር ነው » አለ ሪቻርድ «የገንዘቡ ነገርስ? አንድ መቶ ፓውንድ ነውየምፈልገው »
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...አሮጌዉ ቤት በጨረቃ ብርሃን ሲታይ ጸጥ ቅዝቅዝ ብሎ ነበር " ያንለት ደግሞ ጨረቃዋ በጣም ደምቃለች « በብርሃንዋ ሰፊው ያታክልት ቦታም ዳር እስከ ዳር
ቁልጭ ብሎ ይታያል " በአየር ሁኔታ ማሳያው ያውራ ዶሮ ምሥል በበረንዳውና በባርባራ ላይም በማብራቷ ተለይተው ይታወቃሉ ባርባራ በረንዳውን ቀስ ብላ
አልፋ በፍርሃት ለጭንቀት እንዳፈጠጠች ከአትክልቱ ሥፍራ በታች ወደነበሩት እጅብ ያሉት ዛፎች ወረደች ያ ከዱሩ ወጥቶ እሷን በድብቅ ሲጠቅሳት የነበረው
ፍጡር ሌላ ተጨማሪ መዘዝ ይዞ የመጣ ሰው ይሆን ? ወይም †ፈጥሮው ከሰው የተለየ ልዩ ጉድ ነው ? ወይስ በውን የሌለ በሐሳብ ብቻ የተፈጠረ ባዶ ራዕይ ነው?
የሚሉ ጥያቄዎች በባርባራ አእምሮ ሲተራመሱባት አሁንም ቀረብ ብሎ ጠቀሳት ባርባራ ከፍራቷ የተነሣ እግሮቿ እየተንቀጠቀጡ ያንገት ልብሷን ጭምድድ አድርጋ ያዘች በጠራው ጨረቃ እሷ ወደሱ ስትጠጋ እሱ ደግሞ ወደ ዛፎቹ ጥላ አፈገፈገ" ባርባራ ቆም አለች
« ማነህ ? ምንድነህ ? » አለችው ድምጿን ዝቅ አድርጋ!«ምን ትፈልጋለህ ? »
« ባርባራ » ብሎ ጠራት በሹክሹክታ ድምፅ «አላወቅሽኝም ? » ገና ከመናገሩ
ድምፁ በትክክል ለየችው » ከደስታ ይልቅ ፍራት ያመዘነበት ድምፅ አሰምታ ተንደርድራ ወደሱ ሔዶች » በእርሻ ሥራ የዋለ ገበሬ የሚለብሰውን ዐይነት ልብስ
የለበሰ ሰው በክንዶቹ ዕቅፍ ሲያደርጋት ሥቅሥቅ ብላ አለቀሰች " የሥራ ካፖርት
ደርቦ የሣር ባርኔጣ ደፍቶ ሰው ሠራሽ ሪዝ አድርጎ ፍጹም ሌላ ሰው መስሎ ቢመጣም ወንድሟ መሆኑን ዐወቀችው
« ሪቻርድ ! ከየት መጣህ ? ከዚህ ምን አመጣህ ? እኔ ደግሞ ምናልባት ካንተ የተላከ ሰው እንደሆነ ብዬ ተጠራጠርኰ እንጂ እንደዚህ ሆነህ ትመጣለህ ብዬ
አላሰብኩም " አሁንም በጣም ነው ያስደነገጥኸኝ እውነት በጤናህ ነው ወይስ ዐብደህ የመጣኸው ? እዚህ ብትገኝ ሞት እንደሚጠብቅህ እያወቅህ እንዴት ደፍረሀ ትመጣለህ ? » አለችው እጆቿን እያፋተገች
«ያውም ከወንጀለኛ መስቀያ ላይ ነዋ እንደምገደል መች ጠፋኝ ባርባራ ዐውቀዋለሁ " »
« ታዲያ ለምንድን ነው ወደ መጥፈያህ ስተት ብለህ የመጣህ ? እማማ ብታይህ
በአድራጐትህና በድፍረትህ ደንግጣ ትሞታለች »
« ኑሮውን አልቻልኩትም ከወጣሁ ጀምሮ እስከ ዛሬ ለንደን ስሠራ ነበር ነገር ግን በዚሁ ዐይነት መግፋት አልቻልኩም
" ትንሽ ገንዘብ ባገኝ ግን ከዚህ የተሻለ ዕድል አለኝ " ስለዚህ አማማ ጥቂት ገንዘብ ብትሰጠኝ ለመጠየቅ ነው የመጣሁት»
« እስከ ዛፊ ምን ትሠራ ነበር ? »
« በአንድ የፈረሶች ጋጣ ውስጥ ነበር የምሠራው " »
« ምን ! በፈረሶች ጋጣ ? »
አለችው የእውነቷን ድንግጥ ብላ»
"ከዚህ የተሻለ ምን ዕድል ሊኖረኝ ይችላል ? ነጋዴ ? ባንከኛ ? መይስ የንድ ሚኒስትር ልዩ ጸሐፊ መሆን ? ነው ወይስ ንብረት ኖሮኝ በሀብቴ ልተዳደር?» አላት
የሆዱ ብሶት እየተናነቀው « አየሽ የምተዳደረው በሳምንት በማገኛት
ዐሥራ ሁለት ሽልንግ ብቻ ነው»
« አዬ ሪቻርድ ! » አለች እጁን ግጥም አድርጋ ይዛ እያለቀስች
« እንዴት ያሉ ጐደሎ ቀን ነው ? አየህ ......... እኛ የምንጽናናው ድርጊቱ በደም ፍላት እንጂ
ሆን ብለህ እንዳልፈጸምከው በማሰብ ብቻ ነው»
« ባርባራ እኔ እኮ ምንም ወንጀል አልፈጸምኩም »
« ምን? »
« በውነት እምልልሻለሁ ። ከደሙ ንጹሕ ነኝ እንዳያውም ሰውየው ሲገደል እኔ ከቦታወ አልነበርኩም " እስከማውቀው ድረስ በግምት ካልሆነ በቀር እገሌ ሲገድል አየሁ ብዬ በዐይን ምስክርነት መናገር እንኳ አልችልም " አላየሁም "
ግምቴ ግን ከማየት የማያንስ ትክክለኛ ነው »
ባርባራ አሁን በበላጠ አንዘረዘራት « መቸም ወንጀሉን የፈጸው ቤተል
ማለትህ እንዳልሆነ እርግኛ ነኝ »
« ቤተል ? እሱም በነገሩ የለበትም እሱ ለራሱ በድብቅ አውሬ ያድን
ነበር ፤ ወጥመዶቹን ነበር የሚከታተል »
« እማማ ግን በወንጀሉ የቤተል እጅ አለበት ያለች አላስቀምጠኝ አለች»
« ተሳስታለች እሱን እንድትጠረጥር ያዪረጋት ምንድነው ? »
« ከመጀመሪያ ይህ እምነት እንዴት እንዳደረባት ልነግርህ አልችልም እሷም ራሷ የምታውቀው አይመስለኝም " ወትሮም ቢሆን ምን ያህል ደካማ እንዶሆነችና በሐሳቧ የሚመጣባትን ሁሉ እውነት መስሎ እንደሚታያት አንተም ታስታውሳለህ አሁን ከዚያ አሠቃቂ ምሽት ጀምሮ ስለ ግድያው ሁልጊዜ ሕልም ታየኝ ትላለች በሕልሟ ውስጥ ሁሉ ቤተልም አብሮ ይታያታል " ስለዚህ ቤተል በነገሩ እንዳለበት ያለ ምንም መጠራጠር ታምናለች »
« ባርባራ እሱ በዚህ ጉዳይ አልነበረበትም »
« አንተ እንዳልነበርክበት ነው አሁን የምትነግረኝ ? »
« እኔ በዚያን ጊዜ ከሆሊጆን ቤትም አልነበርኩ " ወንጀሉን የፈጸመ ቶርን ነው»
« ቶርን ? » አለች አንገቷን ቀና አድርጋ « ቶርን ማነው ? »
« እንጃ ! ባውቀው ደስ ይለኝ ነበር ከገባበት መዝዤ ባወጣው በወደድኩ ሰውየው የአፊ ወዳጅ ነበር ። »
“ሪቻርድ !! ... ይህን ስም ስታነሣብኝ ራስህን የዘነጋህ መስልከኝ ” አልችው አንገቷን በቁጣ ወዶ ኋላ ምልስ አድርጋ
«እኔ!ኮ አንድ ጊዜ ያበላሸሁት ስለሆነ በጉዳዩ ለመነጋገር አልሻም " አሁን ስለ ንጽሕናዬ ብናገር ሪቻርድ ሔር ትንሹ በፈጸመው የግፍ ግድያ ተብሎ የተላለፈብኝን ውሳኔ ሊያስለውጥልኝ አይችልም። ግን አባባ ዛሬም እንደ ጠላኝ ነው »
«ከፊቱ ስምህን የሚያነሣ የለም " ከቤት አንድም ሰው ስምህን እንዳይጠራ ለአሽከርቹ በሙሉ ትእዛዝ ሰጥቶአል " ያቺ ኤልሳ መቸም የተነገረችውን ማስታወስ አይሆንላትም " መኝታ ቤትህን የሚስተር ሪቻርድ ክፍል " እያለች ስትናገር ሁለት ጊዜ ቢያስጠነቅቃትም እየረሳች መተው አልቻለችም " በሦስተኛው ከቤት አባረራት ። አባባኮ ምሏል ሰም†ሃል ? »
« ምን ብሎ ? እሱ ሁልጊዜ እንደማለ ነው »
« ያሁኑ ግን ከባድ መሐላ ነው ሪቻርድ።ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ከ0ሥር ዓመት በኋላ ቢገኝ እንኳን አሳልፎ እንደሚሰጥህ ከዳኞቹ ፊት ቁሞ በመማል አረጋግጦላቸዋል እሱ አንድ ጊዜ ከተናገረ እንደማይመለስ ታውቀዋለህ » ስለዚህ ያንተ ከዚህ አካባቢ መገኘት አደገኛ ነው»
« እሱኮ ዱሮውንም እንዶ ልጁ እንዳልቆጠረኝ ሊያደርግልኝ የሚገባውን እንዳላደረገልኝ ዐውቃለሁ » አለ ምርር ባለ አነጋገር « እስኪ አንቺ ስታስቢው
ጤና በማጣቴ ምስኪኗ እናቴ ስለ ተንከባከበችኝ በየደረሰበት ላገኘው ሰው ሁሉ ተሞላቀቀ እያለ ሊያሥቅብኝ ይጥር ነበር እኔ ቢቴ የደስታ ቤት ቢሆንልኝ ኖሮ ይኸ ሁሉ መቸ ይደርስብኝ ነበር ? በይ አሁን ... ...ባርባራ እናቴ ጋር ዐይን ለዐይን ተያይተን መነጋገር አለብን»
ባርባራ ከመናገሯ በፊት ትንሽ አሰበች« እንዴት እንደ ምናሳካው አላውቅም»
« ለምን አንቺ እንደ መጣሺው እሷስ ወደኔ አትመጣም? ለመሆኑ ተኝታለች ወይስ ተነሥታለች ? »
« ዛሬ ከሷ ጋር መተያየት የማይሆን ነገር ነው አባባ ሳናስበው ሊመጣ ይችላል
አሁን ያለው ከቦሻ ቤት ነው»
« ዐሥራ ስምንት ወር ሙሉ ሳንተያይ ኖረን አሁን ደግሞ ሳላገኛት ብሔድ በጣም ከባድ ነገር ነው » አለ ሪቻርድ «የገንዘቡ ነገርስ? አንድ መቶ ፓውንድ ነውየምፈልገው »
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
ወደ ሀብታምነት ጉዞ
እናታችን እቃዎቿን ስታሽግ እኔና ክሪስቶፈር ደግሞ ልብሶቻችንን ከጥቂት አሻንጉሊቶችና ከአንድ መጫወቻ ጋር በሁለት ሻንጣዎች ውስጥ ማጨቅ ጀመርን: በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ጓደኛችንን እንኳን ሳንሰናበት ታክሲ መጥቶ ወደ ባቡር ጣቢያ ወሰደን፡ እናታችን ማንንም ሳንሰናበት
በሚስጥር ሹልክ ብለን እንድንሄድ የግድ ያለችን ለምን እንደሆነ አልገባኝም።
ባቡሩ ብዙ ከተሞችና መንደሮች እንዲሁም እርሻ ቦታ ላይ ያሉ ቤቶችን እያቆራረጠ ወደ ቨርጂኒያ ግዛት ሲያመራ እኔና ወንድሜ አንድም ነገር እንዳያመልጠን ብለን መተኛት አልፈለግንም በዚያ ላይ ብዙ የምናወራችው
ነገሮች ነበሩን፡ ወሬያችን በአብዛኛው ስለዛ ትልቅ የሀብታም ቤት፣ ተንደላቀን ስለመኖር፣በወርቅ ሳህን ስለመመገብና የሚያምር ልብስ በለበሰ ሰራተኛ
ስለመስተናገድ ነበር ልብሶቼን የምታጣጥፍ፣ የገላ ውሀ የምታዘጋጅ፣ ፀጉሬን
የምታበጥርልኝና ባዘዝኳት ቁጥር ከች የምትል የግል ሠራተኛ እንደምትኖረኝ አሰብኩ ግን በጣም ክፉ አልሆንባትም በጣም የምወደውን ዕቃ ካልሰበረችብኝ
በስተቀር ሠራተኞች ሁሉ የሚመኟት አይነት ደግ እመቤት ነው የምሆንላት መቼም የማልወዳቸውንና የማልፈልጋቸውን ነገሮች መጣሌ ስለማይቀር በደንብ ነው የምከፍላት፡
በዚያ ምሽት ባቡሩ ውስጥ እያለን ጨለማውን ወደ ኋላ ስመለከት ምሽቱ ማደግና መፈላሰፍ የጀመርኩበት የመጀመሪያ ምሽት እንደሆነ አስተዋልኩ ሁሉንም ለማግኘት የሆነ ነገር ማጣት ስላለ እኔም የሚመጣውን ልለምደው
እና በጣም ጥሩ ላደርገው ያስፈልጋል እኔና ወንድሜ ገንዘቡ እጃችን ውስጥ ሲገባ በምን እንደምናጠፋው እየተነጋገርን
እያለ ፀጉሩ በመመለጥ ላይ ያለ የባቡሩ ሠራተኛ ወዳለንበት መጣ። የመጣበት ከመናገሩ በፊት እናታችንን በአድናቆት ከእግር እስከራሷ ተመለከታት። ከዚ
“ወ/ሮ ፓተርስን፣ በአስራ አምስት ደቂቃ ውስጥ መውረጃሽ ጋር እንደርሳለን አላት።
አሁን ደግሞ ለምንድነው “ወ/ሮ ፓተርሰን” ብሎ የጠራት? ግራ ገባኝ፡ ክሪስቶፈርን በጥያቄ አይን ተመለከትኩት እሱም ግራ የተጋባ ይመስላል።
ድንገት ስትነቃ የት እንዳለች ግር በመሰኘቷ የእናታችን አይኖች በሀይል ተከፈቱና ትኩረቷ ወደ ባቡሩ ሠራተኛ፣ ቀጥሎ ወደ እኔና ክሪስቶፈር ከዚያ ደግሞ ተስፋ በመቁረጥ እንቅልፍ ውስጥ ወዳሉት መንትዮች ተሻገረ። ወዲያው እምባዋ መጣና ከቦርሳዋ ውስጥ መሀረብ አውጥታ አይኖቿን ጠረገች። ሀዘን
በተሞላበት አይነት በከባዱ ስትተነፍስ ልቤ በሽብር መምታት ጀመረ።
አሁንም ቆሞ በአድናቆት እየተመለከታት ላለው የባቡሩ ሠራተኛ እሺ አመሰግናለሁ አትስጋ፣ ለመውረድ ተዘጋጅተናል” አለችው: የኪስ ስዓቱን ተመለከተና የጭንቀት እይታውን ወደ እኔና ክሪስቶፈር ከዚያ ደግሞ ወደ የተኙት መንትዮች አደረገ። ከዚያ “እመቤቴ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ነው ስትወርዱ የሚጠብቃችሁ ሰው አለ?” አላት።
“ችግር የለም” ስትል እናቴ አረጋገጠችለት።
“እመቤቴ በጣም ጨለማ እኮ ነው”
“የቤቴን መንገድ በእንቅልፍ ልቤ እንኳን አውቀዋለሁ።”
የአያት አይነት ባህርይ ያለው የባቡሩ ሠራተኛ የተናገረችው ነገር አላረካውም። “እመቤት፣ ቻርለትስቪል ከመውረጃችሁ የአንድ ሰዓት መንገድ ነው: አንቺንና ልጆቹን የምናወርዳችሁ ቤት የሚባል ነገር በማይታይበት ቦታ ላይ ነው አላት።
እናቴ ተጨማሪ ጥያቄዎችን ላለመፍቀድ በጣም ትዕቢት በተሞላበት አነጋገር
“የሆነ ሰው ይጠብቀናል” አለችው ባንድ ጊዜ እንዴት እንደዚህ ያለ ባህርይ ልታመጣና ወዲያው ደግሞ ልክ እንደ ኮፍያ በቀላሉ ልታወልቀው እንደቻለች ማየት ያስገርማል።
እውነትም ምንም ነገር በሌለበት ቦታ ደረስን ከባቡሩ ወረድን፡ ከባቡር ስንወርድ ሙሉ በሙሉ ጨለማ ቢሆንም ማንም የጠበቀን አልነበረም: የባቡሩ ሠራተኛ እንዳስጠነቀቀን አንድም የሚታይ ቤት የለም። በጨለማ ብቻችንን
የሰው ፍጥረት በማይታይበት ቆም ብለን የባቡሩ ደረጃ ላይ ለቆመው የባቡሩ ሠራተኛ የስንብት እጃችንን አውለበለብንለት ከገፅታው እንደተረዳሁት “ወ/ሮ ፓተርሰንን” ፦ሤከአራት እያንቀላፉ ካሉ ልጆቿ ጋር ትቶ መሄዱ ደስ አላሰኘውም።
ዙሪያውን ስመለከት ማየት የቻልኩት በአራት የእንጨት ምሰሶዎች የተደገፈ የዛገ የቆርቆሮ ጣራና አረንጓዴ አግዳሚ ወንበር ብቻ ነው፡ የባቡር ጣቢያው
መሆኑ ነው። ባቡሩ በጨለማው ውስጥ እስኪሰወርና መልካም ዕድል እየተመኘልን የሚመስል አንድ አሳዛኝ የጥሩምባ ድምፁን እስክንሰማ ድረስ ቆመን እያየነው ነበር።
በሜዳና በመስኮች ተከበናል ከባቡር መውረጃው ጀርባ ካለው ጫካ ውስጥ የሆነ የተለየ ድምፅ ስሰማ በድንጋጤ ዘለልኩና ምንነቱን ለማወቅ ዙሪያውን
ረስመለከት ክሪስቶፈር ሳቀብኝ።“ጉጉት እኮ ናት! ጣረሞት መስሎሽ ነበር?”
አለኝ።
እናታችን “አሁን ማንም የለም: በሹክሹክታ መናገር የለባችሁም: ይህ የእርሻ ሀገር ነው በአብዛኛው ያሉት የወተት ላሞች ናቸው። ዙሪያውን ተመልከቱ። የስንዴና የአጃ እንዲሁም የገብስ መሬቶች ናቸው። እዚህ ያሉት ገበሬዎች ናቸው ኮረብታው ላይ ለሚኖሩት ሀብታሞች ምርቶቻቸውን በትኩሱ
የሚያቀርቡት”
ተቀጣጥለው የቆሙ በጣም ብዙ ኮረብታዎች ሲኖሩ ኮረብቶቹ ላይ በንፋስ ላይና ታች የሚሉ በርካታ ዛፎችም ተደርድረዋል። የምሽት ዘበኞች ብዬ ጠራኋቸው። እናታችን ግን ተደርድረው የተተከሉት በርካታ ዛፎች ከባዱን
ነፋስ ለመከላከልና ከባድ በረዶ ሲመጣ እንዲይዙ መሆኑን ነገረችን። ንፋስና በረዶ ክሪስቶፈርን የማረኩት ትክክለኛ ቃላት ነበሩ። ምክንያቱም በበረዶ
የሚደረጉ ሁሉንም አይነት የክረምት ስፖርቶች ይወዳል። እና እንደ ቨርጂያ ያለ የደቡብ ክፍል ከባድ በረዶ ይኖረዋል ብሎ አላሰበም።
“እዚህም በረዶ ይጥላል” አለች እናቴ: “ያለነውኮ ከብሉሪች ተራራዎች ስር ነው: ልክ እንደ ግላድስተን እዚህም ብርድ አለ። በበጋ ቀኑ በጣም ይሞቃል፤
ምሽቱ ግን ሁልጊዜም ቢያንስ አንድ ብርድ ልብስ ብቻ የሚያስለብስ ቅዝቃዜ አለው አሁን ፀሀዩዋ ብትወጣ ኖሮ ውብ የሆነውን ገጠር ማየት ትችሉ ነበር።በዓለም ላይ የዚህን ያህል የሚያምር ቦታ የለም አሁን በጣም መፍጠን አለብን ቤት ለመድረስ በጣም ረጅም መንገድ ይጠብቀናል። ከመንጋቱና
ሠራተኞቹ ከመነሳታቸው በፊት መድረስ አለብን፡” አለችን፡።
በጣም ይገርማል፡ “ሰራተኞቹ ከመነሳታቸው በፊት? ለምን? የባቡሩ ሠራተኛ ወ/ሮ ፓተርሰን ብሎ የጠራሽ ለምንድነው?” ብዬ ጠየቅኳት፡፡
"ካቲ አሁን ለአንቺ የማብራራበት ጊዜ የለኝም:: እየፈጠንን መራመድ አለብን አለችና ሁለቱን ከባባድ ሻንጣዎች አንስታ ጠንhር ባለ ድምፅ እንድንከተላት
አዘዘችን፡ እኔና ክሪስቶፈር እንቅልፋቸው ከመምጣቱ የተነሳ ለመራመድ ሙከራ ማድረግ ያልቻሉትን መንትዮቹን ለመሸከም ተገደድን።
ትንሽ እንደተራመድን “እማዬ የባቡሩ ሠራተኛ የአንቺን ሁለት ሻንጣዎጆ ሳይሰጠን ረስቶታል” አልኳት።
“ምንም አይደል ካቲ፤ ሻንጣዎቹን ወስዶ ሻንጣ ክፍል ውስጥ እንዲያደርግልኝ ነገ እንደምወስደው ነግሬዋለሁ” አለችኝ: የያዘቻቸው ሁለት ሻንጣዎች ጥንካሬዋን እንደቀነሱት ሁሉ ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ነበር
“ለምንድነው እንደዚያ ያደረግሽው?” ሲል ጠየቃት ክሪስቶፈር።
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
ወደ ሀብታምነት ጉዞ
እናታችን እቃዎቿን ስታሽግ እኔና ክሪስቶፈር ደግሞ ልብሶቻችንን ከጥቂት አሻንጉሊቶችና ከአንድ መጫወቻ ጋር በሁለት ሻንጣዎች ውስጥ ማጨቅ ጀመርን: በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ጓደኛችንን እንኳን ሳንሰናበት ታክሲ መጥቶ ወደ ባቡር ጣቢያ ወሰደን፡ እናታችን ማንንም ሳንሰናበት
በሚስጥር ሹልክ ብለን እንድንሄድ የግድ ያለችን ለምን እንደሆነ አልገባኝም።
ባቡሩ ብዙ ከተሞችና መንደሮች እንዲሁም እርሻ ቦታ ላይ ያሉ ቤቶችን እያቆራረጠ ወደ ቨርጂኒያ ግዛት ሲያመራ እኔና ወንድሜ አንድም ነገር እንዳያመልጠን ብለን መተኛት አልፈለግንም በዚያ ላይ ብዙ የምናወራችው
ነገሮች ነበሩን፡ ወሬያችን በአብዛኛው ስለዛ ትልቅ የሀብታም ቤት፣ ተንደላቀን ስለመኖር፣በወርቅ ሳህን ስለመመገብና የሚያምር ልብስ በለበሰ ሰራተኛ
ስለመስተናገድ ነበር ልብሶቼን የምታጣጥፍ፣ የገላ ውሀ የምታዘጋጅ፣ ፀጉሬን
የምታበጥርልኝና ባዘዝኳት ቁጥር ከች የምትል የግል ሠራተኛ እንደምትኖረኝ አሰብኩ ግን በጣም ክፉ አልሆንባትም በጣም የምወደውን ዕቃ ካልሰበረችብኝ
በስተቀር ሠራተኞች ሁሉ የሚመኟት አይነት ደግ እመቤት ነው የምሆንላት መቼም የማልወዳቸውንና የማልፈልጋቸውን ነገሮች መጣሌ ስለማይቀር በደንብ ነው የምከፍላት፡
በዚያ ምሽት ባቡሩ ውስጥ እያለን ጨለማውን ወደ ኋላ ስመለከት ምሽቱ ማደግና መፈላሰፍ የጀመርኩበት የመጀመሪያ ምሽት እንደሆነ አስተዋልኩ ሁሉንም ለማግኘት የሆነ ነገር ማጣት ስላለ እኔም የሚመጣውን ልለምደው
እና በጣም ጥሩ ላደርገው ያስፈልጋል እኔና ወንድሜ ገንዘቡ እጃችን ውስጥ ሲገባ በምን እንደምናጠፋው እየተነጋገርን
እያለ ፀጉሩ በመመለጥ ላይ ያለ የባቡሩ ሠራተኛ ወዳለንበት መጣ። የመጣበት ከመናገሩ በፊት እናታችንን በአድናቆት ከእግር እስከራሷ ተመለከታት። ከዚ
“ወ/ሮ ፓተርስን፣ በአስራ አምስት ደቂቃ ውስጥ መውረጃሽ ጋር እንደርሳለን አላት።
አሁን ደግሞ ለምንድነው “ወ/ሮ ፓተርሰን” ብሎ የጠራት? ግራ ገባኝ፡ ክሪስቶፈርን በጥያቄ አይን ተመለከትኩት እሱም ግራ የተጋባ ይመስላል።
ድንገት ስትነቃ የት እንዳለች ግር በመሰኘቷ የእናታችን አይኖች በሀይል ተከፈቱና ትኩረቷ ወደ ባቡሩ ሠራተኛ፣ ቀጥሎ ወደ እኔና ክሪስቶፈር ከዚያ ደግሞ ተስፋ በመቁረጥ እንቅልፍ ውስጥ ወዳሉት መንትዮች ተሻገረ። ወዲያው እምባዋ መጣና ከቦርሳዋ ውስጥ መሀረብ አውጥታ አይኖቿን ጠረገች። ሀዘን
በተሞላበት አይነት በከባዱ ስትተነፍስ ልቤ በሽብር መምታት ጀመረ።
አሁንም ቆሞ በአድናቆት እየተመለከታት ላለው የባቡሩ ሠራተኛ እሺ አመሰግናለሁ አትስጋ፣ ለመውረድ ተዘጋጅተናል” አለችው: የኪስ ስዓቱን ተመለከተና የጭንቀት እይታውን ወደ እኔና ክሪስቶፈር ከዚያ ደግሞ ወደ የተኙት መንትዮች አደረገ። ከዚያ “እመቤቴ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ነው ስትወርዱ የሚጠብቃችሁ ሰው አለ?” አላት።
“ችግር የለም” ስትል እናቴ አረጋገጠችለት።
“እመቤቴ በጣም ጨለማ እኮ ነው”
“የቤቴን መንገድ በእንቅልፍ ልቤ እንኳን አውቀዋለሁ።”
የአያት አይነት ባህርይ ያለው የባቡሩ ሠራተኛ የተናገረችው ነገር አላረካውም። “እመቤት፣ ቻርለትስቪል ከመውረጃችሁ የአንድ ሰዓት መንገድ ነው: አንቺንና ልጆቹን የምናወርዳችሁ ቤት የሚባል ነገር በማይታይበት ቦታ ላይ ነው አላት።
እናቴ ተጨማሪ ጥያቄዎችን ላለመፍቀድ በጣም ትዕቢት በተሞላበት አነጋገር
“የሆነ ሰው ይጠብቀናል” አለችው ባንድ ጊዜ እንዴት እንደዚህ ያለ ባህርይ ልታመጣና ወዲያው ደግሞ ልክ እንደ ኮፍያ በቀላሉ ልታወልቀው እንደቻለች ማየት ያስገርማል።
እውነትም ምንም ነገር በሌለበት ቦታ ደረስን ከባቡሩ ወረድን፡ ከባቡር ስንወርድ ሙሉ በሙሉ ጨለማ ቢሆንም ማንም የጠበቀን አልነበረም: የባቡሩ ሠራተኛ እንዳስጠነቀቀን አንድም የሚታይ ቤት የለም። በጨለማ ብቻችንን
የሰው ፍጥረት በማይታይበት ቆም ብለን የባቡሩ ደረጃ ላይ ለቆመው የባቡሩ ሠራተኛ የስንብት እጃችንን አውለበለብንለት ከገፅታው እንደተረዳሁት “ወ/ሮ ፓተርሰንን” ፦ሤከአራት እያንቀላፉ ካሉ ልጆቿ ጋር ትቶ መሄዱ ደስ አላሰኘውም።
ዙሪያውን ስመለከት ማየት የቻልኩት በአራት የእንጨት ምሰሶዎች የተደገፈ የዛገ የቆርቆሮ ጣራና አረንጓዴ አግዳሚ ወንበር ብቻ ነው፡ የባቡር ጣቢያው
መሆኑ ነው። ባቡሩ በጨለማው ውስጥ እስኪሰወርና መልካም ዕድል እየተመኘልን የሚመስል አንድ አሳዛኝ የጥሩምባ ድምፁን እስክንሰማ ድረስ ቆመን እያየነው ነበር።
በሜዳና በመስኮች ተከበናል ከባቡር መውረጃው ጀርባ ካለው ጫካ ውስጥ የሆነ የተለየ ድምፅ ስሰማ በድንጋጤ ዘለልኩና ምንነቱን ለማወቅ ዙሪያውን
ረስመለከት ክሪስቶፈር ሳቀብኝ።“ጉጉት እኮ ናት! ጣረሞት መስሎሽ ነበር?”
አለኝ።
እናታችን “አሁን ማንም የለም: በሹክሹክታ መናገር የለባችሁም: ይህ የእርሻ ሀገር ነው በአብዛኛው ያሉት የወተት ላሞች ናቸው። ዙሪያውን ተመልከቱ። የስንዴና የአጃ እንዲሁም የገብስ መሬቶች ናቸው። እዚህ ያሉት ገበሬዎች ናቸው ኮረብታው ላይ ለሚኖሩት ሀብታሞች ምርቶቻቸውን በትኩሱ
የሚያቀርቡት”
ተቀጣጥለው የቆሙ በጣም ብዙ ኮረብታዎች ሲኖሩ ኮረብቶቹ ላይ በንፋስ ላይና ታች የሚሉ በርካታ ዛፎችም ተደርድረዋል። የምሽት ዘበኞች ብዬ ጠራኋቸው። እናታችን ግን ተደርድረው የተተከሉት በርካታ ዛፎች ከባዱን
ነፋስ ለመከላከልና ከባድ በረዶ ሲመጣ እንዲይዙ መሆኑን ነገረችን። ንፋስና በረዶ ክሪስቶፈርን የማረኩት ትክክለኛ ቃላት ነበሩ። ምክንያቱም በበረዶ
የሚደረጉ ሁሉንም አይነት የክረምት ስፖርቶች ይወዳል። እና እንደ ቨርጂያ ያለ የደቡብ ክፍል ከባድ በረዶ ይኖረዋል ብሎ አላሰበም።
“እዚህም በረዶ ይጥላል” አለች እናቴ: “ያለነውኮ ከብሉሪች ተራራዎች ስር ነው: ልክ እንደ ግላድስተን እዚህም ብርድ አለ። በበጋ ቀኑ በጣም ይሞቃል፤
ምሽቱ ግን ሁልጊዜም ቢያንስ አንድ ብርድ ልብስ ብቻ የሚያስለብስ ቅዝቃዜ አለው አሁን ፀሀዩዋ ብትወጣ ኖሮ ውብ የሆነውን ገጠር ማየት ትችሉ ነበር።በዓለም ላይ የዚህን ያህል የሚያምር ቦታ የለም አሁን በጣም መፍጠን አለብን ቤት ለመድረስ በጣም ረጅም መንገድ ይጠብቀናል። ከመንጋቱና
ሠራተኞቹ ከመነሳታቸው በፊት መድረስ አለብን፡” አለችን፡።
በጣም ይገርማል፡ “ሰራተኞቹ ከመነሳታቸው በፊት? ለምን? የባቡሩ ሠራተኛ ወ/ሮ ፓተርሰን ብሎ የጠራሽ ለምንድነው?” ብዬ ጠየቅኳት፡፡
"ካቲ አሁን ለአንቺ የማብራራበት ጊዜ የለኝም:: እየፈጠንን መራመድ አለብን አለችና ሁለቱን ከባባድ ሻንጣዎች አንስታ ጠንhር ባለ ድምፅ እንድንከተላት
አዘዘችን፡ እኔና ክሪስቶፈር እንቅልፋቸው ከመምጣቱ የተነሳ ለመራመድ ሙከራ ማድረግ ያልቻሉትን መንትዮቹን ለመሸከም ተገደድን።
ትንሽ እንደተራመድን “እማዬ የባቡሩ ሠራተኛ የአንቺን ሁለት ሻንጣዎጆ ሳይሰጠን ረስቶታል” አልኳት።
“ምንም አይደል ካቲ፤ ሻንጣዎቹን ወስዶ ሻንጣ ክፍል ውስጥ እንዲያደርግልኝ ነገ እንደምወስደው ነግሬዋለሁ” አለችኝ: የያዘቻቸው ሁለት ሻንጣዎች ጥንካሬዋን እንደቀነሱት ሁሉ ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ነበር
“ለምንድነው እንደዚያ ያደረግሽው?” ሲል ጠየቃት ክሪስቶፈር።
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
...ለሁለት ቀን ቤርጎ ትከራይና በሚቀጥለው ቀን ትወጣለች ምድር ጦር
መምሪያ ተመዝግባ ለሆቱሉ በመደወል የሆቴል ኪራዩን ደረሰኝ ለአባቷ ጠበቃ እንዲላክ ታደርጋለች፡
በረጅሙ ተነፈሰችና በሩን ከፍታ ገባች፡፡
ማርጋሬት በቀጥታ ወደ እንግዳ ተቀባዩ አመራች ከፍተኛ እረፍት ተሰማት። ፍርሃትና ቅዠቱ አብቅቷል።
አንድ ወጣት እንግዳ ተቀባይ ባንኮኒ ተደግፎ ያንጎላጃል። ማርጋሬት
‹‹እህምም›› ብላ ጉሮሮዋን ስትጠራርግ ወጣቱ ነቃ ድንጋጤ እና መደናገር
ፊቱ ላይ ይታያል።
‹‹ቤርጎ አላችሁ?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹በዚህ ሰዓት?›› ሲል መለሰ።
‹‹ጨለማው አላስኬድ አለኝና እቤት መሄድ አልቻልኩም››
ወጣቱ ራሱን ገዛና ‹‹ሻንጣሽ የታለ?›› ሲል ጠየቃት።
<<የለኝም›› አለች ማርጋሬት በማፈር፧ ከዚያም አሰብ አደረገችና
‹‹የለኝም ጨለማው አያስኬደኝም ብዬ አላሰብኩም ነበር›› አለች
ወጣቱ ሁለመናዋን አስተዋለ። ፊቱን ደባበሰና መዝገቡን የሚያይ
መሰለ። ሰውዬው ምን ነካው? ስትል አሰበች።
‹‹ቦታ የለንም›› አላት።
‹‹አላችሁ››
‹‹ከአባትሽ ጋር ተጣልተሽ ነው አይደለም?›› አላት እየጠቀሳት።
‹‹አይደለም፣ እቤት መሄድ ስላልቻልኩ ነው›› ስትል ደገመች።
‹‹ታዲያ ምን ላድርግ ሂትለርን ጠይቂ››
ልጅነቱን አየችና ‹‹አለቃህ የት ነው?›› አለችው፡
የተሰደበ መሰለው ‹‹እስከ ጧቱ 12፡00 ሰዓት እኔ ነኝ ኃላፊው›› አላት
ማርጋሬት ዙሪያውን አየችና ‹‹እስኪነጋ እዚሁ እቀመጣለሁ›› አለች
በመሰላቸት፡
‹‹አይቻልም!›› አለ ወጣቱ ፈርቶ ሻንጣ ያልያዘች ኮረዳ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ልታድር?› ሲል አሰበና ‹ቀዚህ ምክንያት ከስራ እባረራለሁ›› አላት።
‹‹እኔ ኮረዳ አይደለሁም›› አለች ብልጭ ብሎባት፤‹‹እኔ እመቤት ኦክሰንፎርድ ነኝ›› ማዕረጓን መጠቀም አልፈለገችም ነበር፤ ምን ታድርግ፡
ይህን ብትልም ምንም አልጠቀማትም፡ እንግዳ ተቀባዩ ገላመጣትና
‹‹ትቀልጃለሽ!›› አላት በማሽሟጠጥ።ማርጋሬትም ልትጮህበት አሰበችና መልኳን በመስታወት ስታይ ዓይኗ እንደጠቆረ ተገነዘበች ከዚያም በላይ እጇ ቆሽሿል፤ ቀሚሷም ተቀዳል፡
እንግዳ ተቀባዩ ቦታ የለንም ማለቱ አያስደንቅም: በተስፋ መቁረጥ ‹‹መቼም
ጨለማ ውስጥ ሂጂ አትለኝም!›› አለችው:
‹‹ከዚህ ሌላ የምልሽ የለም›› አላት።
ማርጋሬት ዝም ብዬ ብቀመጥና ከዚህ አልነቃነቅም ብል እንግዴ
ተቀባዩ ምን ይለኝ ይሆን? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ይኸው ነው ማለት የፈለገችው ምክንያቱም በጣም ደክሟታል፤ ሰውነቷም ዝሏል ለጠብ
የሚሆን ጉልበት የላትም፡፡ ከዚህም በላይ ውድቅት በመሆኑ ወጣቱ ምን
እንደሚያደርጋት አይታወቅም፡፡
ሰውነቷ እንደዛለ ጀርባዋን ሰጥታው እንደከፋት ወጥታ ጨለማ ውስጥ ገባች፡፡ እየሄደችም ከእንግዳ ተቀባዩ ጋር ልጣላ ይሆን?› ስትል ነገር ስታስብ ይበልጥ ኃይል ያላት የሚመስላት? አሁን እጅ ከሰጠች በኋላ
አሰበች፡፡ ግን ለምንድ ነው ከምታደርገው ይልቅ ማድረግ የምትፈልገው
ይበልጥ መናደዷ ገረማት፡፡ እንደ ንዴቷ ከሆነ ከእንግዳ ተቀባዩ ጋር ትጣላ ነበር፡፡ ተመልሳ ለመሄድ ፈለገች፡ ሆኖም ወደፊት መራመዷን ቀጠለች:: አዎን መሄዱ ነው የሚሻለው፡፡
ዳሩ ምንም መሄጃ የላትም፡፡ ከእንግዲህ የካትሪንን ቤት ማግኘት አትችልም፡፡ የአክስቷ ቤት ጠፍቶባታል፡ ሌሎች ዘመዶቿን አታምናቸውም ሰውነቷ ስለቆሸሽም ቤርጎ ማግኘት አልቻለችም፡
እስኪነጋ መዞር ትችላለች፡፡ አየሩ ጥሩ ነው፡፡ ዝናብ ስለሌለም ብዙም
አይበርድም፡፡ ያለማቋረጥ ከተራመደችም አይበርዳትም አሁን ያለችበት መንገድ ላይ ብዙ የትራፊክ መብራት ስላለ የምትሄድበትን መንገድ ማየት ትችላለች በየደቂቃው መኪና ይተላለፋል፡፡ ከየምሽት ክበቡ ሙዚቃና ሁካታ ይሰማታል፡፡ በየመንገዱ ሽክ ያሉ ሴቶችና በየፓርቲው ያመሹ ሱፍ ግጥም አድርገው የለበሱ ወንዶች በሾፌር በሚነዱ መኪኖች ሲሄዱ ታያለች፡፡ አለፍ እንዳለች ሶስት ብቸኛ ሴቶች አየች፣ አንዷ በር ላይ ሌላዋ ደግሞ ስልክ እንጨት ተደግፋ ቆማለች፣ ሶስተኛዋ መኪና ውስጥ ቁጭ ብላለች፡፡ በአንድ ወቅት እናቷ ኑሮ የጨለመባቸው ሴቶች ያሏት እነዚህን ሳይሆን አይቀርም፡
ድካም ተሰማት ጫማዋ ከቤት እንደወጣች ያደረገችው ነጠላ ጫማ
ነው: ያገኘችው ደጃፍ ላይ ቁጭ አለችና ጫማዋን አውልቃ እግሯን
አከከች።
ቀና ስትል ከመንገዱ ባሻገር ያለው ህንፃ ቅርፅ በመጠኑ ታያት፡፡ እየነጋ ይሆን? በጧት የሚከፈት ሻይ ቤት ታገኝ ይሆናል። ለቁርስ የምድር ጦር መምሪያው የምግብ ክፍል እስኪከፈት ትቆያለች፡፡ ምግብ ከበላች ረጅም ጊዜ በመቆጠሩ የአሳማ ስጋና እንቁላል ትዝ ሲላት በአፏ ምራቋ ሞላ፡፡
ድንገት ቁልቁል የሚያያት አመድ የመሰለ ፊት ድቅን አለባት በድንጋጤ ጮኸች፡፡ ሰውዬው ወጣት ነው፡ ታዲያስ ቆንጂት›› አላት፡
እመር ብላ ተነሳች፡፡ ሰካራም አትወድም፡፡ እነሱ ክብራቸውን የሸጡ ናቸው፡፡ ‹‹ሂድ ጥፋ ከዚህ!›› አለች ቆጣ ብላ፤ ድምጿ ግን ይንቀጠቀጣል፡ቀስ እያለ ተጠጋት ‹‹ታዲያ ሳሚኛ›› አላት፡፡
‹‹አላደርገውም!›› አለች በንዴት ከእሱ ለመሸሽ ወደኋላዋ ስትሄድ ጫማዋ ወለቀባት፡፡ ዞር ብላ ጫማዋን ፍለጋ ስታጎነብስ ወጣቱ አስካካና እጁን ጭኖቿ መሀል ሰዶ ጎነታተላት፡፡ ጫማዋን ይዛ በፍጥነት ቀጥ ብላ
ቆመችና ‹‹ሂድ ከአጠገቤ›› ብላ ጮኸች፡፡
እንደገና ሳቀባትና ‹‹ልክ ነሽ፤ ሴቶች እምቢ ሲሉኝ ደስ ይለኛል›› አለና
የጠጣውን አልኮል ሲተነፍስባት አቅለሸለሻት፡፡ አንቆ አፏን ግጥም አድርጎ
ሳማት፡፡
ሁኔታው ሁሉ የሚያስጠላ ነው፤ ሆዷ ታወከ፡፡ አጥብቆ ስለያዛት ለመታገል ቀርቶ ለመተንፈስ አቃታት፡፡ ለማምለጥ ሙከራ ብታደርግም ለሀጩን እያዝረበረበ ይስማታል፡፡ ከዚያም አንድ እጁን ወደ ጡቷ ሰደደና በእጁ ሲጨመድደው ላንቃዋ እስኪላቀቅ ጩኸቷን ለቀቀችው፡፡
‹‹ደህና፧ ልጎዳሽ አይደለም፧ አታምርሪ›› አላት፡፡ እሷ ግን ጩኸቷን ቀጠለች፡ ሰዎች ከየቦታው ብቅ ብቅ አሉ፡ ሰካራሙ ሰው መምጣቱን ሲያይ ጨለማው ውስጥ ገብቶ ተሰወረ፡ ማርጋሬትም ጩኸቷን አቁማ ለቅሶዋን
ተያያዘችው፡:
አንድ ፖሊስ ባትሪውን እያበራ መጣና ፊቷ ላይ አበራባት፡፡ ከተሰበሰቡት ሰዎች መሀል አንዲት ሴተኛ አዳሪ ‹‹እቺ ልጅ ሽሌ አይደለችም›› አለችው ፖሊሱን፡፡
ፖሊሱ ‹‹ስምሽ ማነው ልጅት?›› አላት
‹‹ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ››
‹‹እመቤት ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ ነሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
ማርጋሬት ንፍጧን ወደ ውስጥ ሳበችና ራሷን ነቀነቀች በአዎንታ
‹‹ነግሬሃለሁ አይደል! ሸሌ አይደለችም›› አለችው ሴተኛ አዳሪዋ፡፡
‹‹ነይ እንሂድ የኔ እመቤት፣ አይዞሽ›› አላት በማጽናናት፡፡
ማርጋሬት በእጅጌዋ ፊቷን ጠርጋ ተነሳች፡:
ፖሊሱ ባትሪውን እያበራ አብረው ሄዱ፡በፍርሃት እየተርገፈገፈች ‹‹ሰውዬው እንዴት ያስፈራል!›› አለች፡፡
‹‹ሀዘኔታ የጎደለው ነው እሱ ምን ይፈረድበታል›› አለ ፖሊሱ ሳቅ እያለ፡፡ ‹‹ይህ ቦታ ከለንደን መንገዶች ሁሉ አደገኛው ነው፡፡ በዚህ ሰዓት
የምትጓዝ ሴት የምሽቱ እመቤት የሆነች ሴት ብቻ ናት፡››
ማርጋሬት ፖሊሱ ያለው ትክክል ነው አለች በሆዷ፡
‹‹ትኩስ ሻይ እንሰጥሽና ብርዱ ለቀቅ ያደርግሻል›› አላት ወደ ጣቢያው ገቡ፡፡ ከባንኮኒው ኋላ ሁለት ፖሊሶች ይታያሉ፡ አንዱ
ጎልማሳና ወደል ሲሆን ሌላው ደግሞ ወጣትና ከሲታ ነው፡፡ ክፍሉ ከጥግ
እስከ ጥግ በእንጨት ባንኮኒ ተገጥግጧል፡፡ ጣቢያው ውስጥ አንዲተ ሴት ትታያለች፡፡
‹‹እዚህ ቁጭ በይ›› አላት ፖሊሱ፡፡ማርጋሬት ተቀመጠች
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
...ለሁለት ቀን ቤርጎ ትከራይና በሚቀጥለው ቀን ትወጣለች ምድር ጦር
መምሪያ ተመዝግባ ለሆቱሉ በመደወል የሆቴል ኪራዩን ደረሰኝ ለአባቷ ጠበቃ እንዲላክ ታደርጋለች፡
በረጅሙ ተነፈሰችና በሩን ከፍታ ገባች፡፡
ማርጋሬት በቀጥታ ወደ እንግዳ ተቀባዩ አመራች ከፍተኛ እረፍት ተሰማት። ፍርሃትና ቅዠቱ አብቅቷል።
አንድ ወጣት እንግዳ ተቀባይ ባንኮኒ ተደግፎ ያንጎላጃል። ማርጋሬት
‹‹እህምም›› ብላ ጉሮሮዋን ስትጠራርግ ወጣቱ ነቃ ድንጋጤ እና መደናገር
ፊቱ ላይ ይታያል።
‹‹ቤርጎ አላችሁ?›› ስትል ጠየቀችው፡
‹‹በዚህ ሰዓት?›› ሲል መለሰ።
‹‹ጨለማው አላስኬድ አለኝና እቤት መሄድ አልቻልኩም››
ወጣቱ ራሱን ገዛና ‹‹ሻንጣሽ የታለ?›› ሲል ጠየቃት።
<<የለኝም›› አለች ማርጋሬት በማፈር፧ ከዚያም አሰብ አደረገችና
‹‹የለኝም ጨለማው አያስኬደኝም ብዬ አላሰብኩም ነበር›› አለች
ወጣቱ ሁለመናዋን አስተዋለ። ፊቱን ደባበሰና መዝገቡን የሚያይ
መሰለ። ሰውዬው ምን ነካው? ስትል አሰበች።
‹‹ቦታ የለንም›› አላት።
‹‹አላችሁ››
‹‹ከአባትሽ ጋር ተጣልተሽ ነው አይደለም?›› አላት እየጠቀሳት።
‹‹አይደለም፣ እቤት መሄድ ስላልቻልኩ ነው›› ስትል ደገመች።
‹‹ታዲያ ምን ላድርግ ሂትለርን ጠይቂ››
ልጅነቱን አየችና ‹‹አለቃህ የት ነው?›› አለችው፡
የተሰደበ መሰለው ‹‹እስከ ጧቱ 12፡00 ሰዓት እኔ ነኝ ኃላፊው›› አላት
ማርጋሬት ዙሪያውን አየችና ‹‹እስኪነጋ እዚሁ እቀመጣለሁ›› አለች
በመሰላቸት፡
‹‹አይቻልም!›› አለ ወጣቱ ፈርቶ ሻንጣ ያልያዘች ኮረዳ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ልታድር?› ሲል አሰበና ‹ቀዚህ ምክንያት ከስራ እባረራለሁ›› አላት።
‹‹እኔ ኮረዳ አይደለሁም›› አለች ብልጭ ብሎባት፤‹‹እኔ እመቤት ኦክሰንፎርድ ነኝ›› ማዕረጓን መጠቀም አልፈለገችም ነበር፤ ምን ታድርግ፡
ይህን ብትልም ምንም አልጠቀማትም፡ እንግዳ ተቀባዩ ገላመጣትና
‹‹ትቀልጃለሽ!›› አላት በማሽሟጠጥ።ማርጋሬትም ልትጮህበት አሰበችና መልኳን በመስታወት ስታይ ዓይኗ እንደጠቆረ ተገነዘበች ከዚያም በላይ እጇ ቆሽሿል፤ ቀሚሷም ተቀዳል፡
እንግዳ ተቀባዩ ቦታ የለንም ማለቱ አያስደንቅም: በተስፋ መቁረጥ ‹‹መቼም
ጨለማ ውስጥ ሂጂ አትለኝም!›› አለችው:
‹‹ከዚህ ሌላ የምልሽ የለም›› አላት።
ማርጋሬት ዝም ብዬ ብቀመጥና ከዚህ አልነቃነቅም ብል እንግዴ
ተቀባዩ ምን ይለኝ ይሆን? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ ይኸው ነው ማለት የፈለገችው ምክንያቱም በጣም ደክሟታል፤ ሰውነቷም ዝሏል ለጠብ
የሚሆን ጉልበት የላትም፡፡ ከዚህም በላይ ውድቅት በመሆኑ ወጣቱ ምን
እንደሚያደርጋት አይታወቅም፡፡
ሰውነቷ እንደዛለ ጀርባዋን ሰጥታው እንደከፋት ወጥታ ጨለማ ውስጥ ገባች፡፡ እየሄደችም ከእንግዳ ተቀባዩ ጋር ልጣላ ይሆን?› ስትል ነገር ስታስብ ይበልጥ ኃይል ያላት የሚመስላት? አሁን እጅ ከሰጠች በኋላ
አሰበች፡፡ ግን ለምንድ ነው ከምታደርገው ይልቅ ማድረግ የምትፈልገው
ይበልጥ መናደዷ ገረማት፡፡ እንደ ንዴቷ ከሆነ ከእንግዳ ተቀባዩ ጋር ትጣላ ነበር፡፡ ተመልሳ ለመሄድ ፈለገች፡ ሆኖም ወደፊት መራመዷን ቀጠለች:: አዎን መሄዱ ነው የሚሻለው፡፡
ዳሩ ምንም መሄጃ የላትም፡፡ ከእንግዲህ የካትሪንን ቤት ማግኘት አትችልም፡፡ የአክስቷ ቤት ጠፍቶባታል፡ ሌሎች ዘመዶቿን አታምናቸውም ሰውነቷ ስለቆሸሽም ቤርጎ ማግኘት አልቻለችም፡
እስኪነጋ መዞር ትችላለች፡፡ አየሩ ጥሩ ነው፡፡ ዝናብ ስለሌለም ብዙም
አይበርድም፡፡ ያለማቋረጥ ከተራመደችም አይበርዳትም አሁን ያለችበት መንገድ ላይ ብዙ የትራፊክ መብራት ስላለ የምትሄድበትን መንገድ ማየት ትችላለች በየደቂቃው መኪና ይተላለፋል፡፡ ከየምሽት ክበቡ ሙዚቃና ሁካታ ይሰማታል፡፡ በየመንገዱ ሽክ ያሉ ሴቶችና በየፓርቲው ያመሹ ሱፍ ግጥም አድርገው የለበሱ ወንዶች በሾፌር በሚነዱ መኪኖች ሲሄዱ ታያለች፡፡ አለፍ እንዳለች ሶስት ብቸኛ ሴቶች አየች፣ አንዷ በር ላይ ሌላዋ ደግሞ ስልክ እንጨት ተደግፋ ቆማለች፣ ሶስተኛዋ መኪና ውስጥ ቁጭ ብላለች፡፡ በአንድ ወቅት እናቷ ኑሮ የጨለመባቸው ሴቶች ያሏት እነዚህን ሳይሆን አይቀርም፡
ድካም ተሰማት ጫማዋ ከቤት እንደወጣች ያደረገችው ነጠላ ጫማ
ነው: ያገኘችው ደጃፍ ላይ ቁጭ አለችና ጫማዋን አውልቃ እግሯን
አከከች።
ቀና ስትል ከመንገዱ ባሻገር ያለው ህንፃ ቅርፅ በመጠኑ ታያት፡፡ እየነጋ ይሆን? በጧት የሚከፈት ሻይ ቤት ታገኝ ይሆናል። ለቁርስ የምድር ጦር መምሪያው የምግብ ክፍል እስኪከፈት ትቆያለች፡፡ ምግብ ከበላች ረጅም ጊዜ በመቆጠሩ የአሳማ ስጋና እንቁላል ትዝ ሲላት በአፏ ምራቋ ሞላ፡፡
ድንገት ቁልቁል የሚያያት አመድ የመሰለ ፊት ድቅን አለባት በድንጋጤ ጮኸች፡፡ ሰውዬው ወጣት ነው፡ ታዲያስ ቆንጂት›› አላት፡
እመር ብላ ተነሳች፡፡ ሰካራም አትወድም፡፡ እነሱ ክብራቸውን የሸጡ ናቸው፡፡ ‹‹ሂድ ጥፋ ከዚህ!›› አለች ቆጣ ብላ፤ ድምጿ ግን ይንቀጠቀጣል፡ቀስ እያለ ተጠጋት ‹‹ታዲያ ሳሚኛ›› አላት፡፡
‹‹አላደርገውም!›› አለች በንዴት ከእሱ ለመሸሽ ወደኋላዋ ስትሄድ ጫማዋ ወለቀባት፡፡ ዞር ብላ ጫማዋን ፍለጋ ስታጎነብስ ወጣቱ አስካካና እጁን ጭኖቿ መሀል ሰዶ ጎነታተላት፡፡ ጫማዋን ይዛ በፍጥነት ቀጥ ብላ
ቆመችና ‹‹ሂድ ከአጠገቤ›› ብላ ጮኸች፡፡
እንደገና ሳቀባትና ‹‹ልክ ነሽ፤ ሴቶች እምቢ ሲሉኝ ደስ ይለኛል›› አለና
የጠጣውን አልኮል ሲተነፍስባት አቅለሸለሻት፡፡ አንቆ አፏን ግጥም አድርጎ
ሳማት፡፡
ሁኔታው ሁሉ የሚያስጠላ ነው፤ ሆዷ ታወከ፡፡ አጥብቆ ስለያዛት ለመታገል ቀርቶ ለመተንፈስ አቃታት፡፡ ለማምለጥ ሙከራ ብታደርግም ለሀጩን እያዝረበረበ ይስማታል፡፡ ከዚያም አንድ እጁን ወደ ጡቷ ሰደደና በእጁ ሲጨመድደው ላንቃዋ እስኪላቀቅ ጩኸቷን ለቀቀችው፡፡
‹‹ደህና፧ ልጎዳሽ አይደለም፧ አታምርሪ›› አላት፡፡ እሷ ግን ጩኸቷን ቀጠለች፡ ሰዎች ከየቦታው ብቅ ብቅ አሉ፡ ሰካራሙ ሰው መምጣቱን ሲያይ ጨለማው ውስጥ ገብቶ ተሰወረ፡ ማርጋሬትም ጩኸቷን አቁማ ለቅሶዋን
ተያያዘችው፡:
አንድ ፖሊስ ባትሪውን እያበራ መጣና ፊቷ ላይ አበራባት፡፡ ከተሰበሰቡት ሰዎች መሀል አንዲት ሴተኛ አዳሪ ‹‹እቺ ልጅ ሽሌ አይደለችም›› አለችው ፖሊሱን፡፡
ፖሊሱ ‹‹ስምሽ ማነው ልጅት?›› አላት
‹‹ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ››
‹‹እመቤት ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ ነሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
ማርጋሬት ንፍጧን ወደ ውስጥ ሳበችና ራሷን ነቀነቀች በአዎንታ
‹‹ነግሬሃለሁ አይደል! ሸሌ አይደለችም›› አለችው ሴተኛ አዳሪዋ፡፡
‹‹ነይ እንሂድ የኔ እመቤት፣ አይዞሽ›› አላት በማጽናናት፡፡
ማርጋሬት በእጅጌዋ ፊቷን ጠርጋ ተነሳች፡:
ፖሊሱ ባትሪውን እያበራ አብረው ሄዱ፡በፍርሃት እየተርገፈገፈች ‹‹ሰውዬው እንዴት ያስፈራል!›› አለች፡፡
‹‹ሀዘኔታ የጎደለው ነው እሱ ምን ይፈረድበታል›› አለ ፖሊሱ ሳቅ እያለ፡፡ ‹‹ይህ ቦታ ከለንደን መንገዶች ሁሉ አደገኛው ነው፡፡ በዚህ ሰዓት
የምትጓዝ ሴት የምሽቱ እመቤት የሆነች ሴት ብቻ ናት፡››
ማርጋሬት ፖሊሱ ያለው ትክክል ነው አለች በሆዷ፡
‹‹ትኩስ ሻይ እንሰጥሽና ብርዱ ለቀቅ ያደርግሻል›› አላት ወደ ጣቢያው ገቡ፡፡ ከባንኮኒው ኋላ ሁለት ፖሊሶች ይታያሉ፡ አንዱ
ጎልማሳና ወደል ሲሆን ሌላው ደግሞ ወጣትና ከሲታ ነው፡፡ ክፍሉ ከጥግ
እስከ ጥግ በእንጨት ባንኮኒ ተገጥግጧል፡፡ ጣቢያው ውስጥ አንዲተ ሴት ትታያለች፡፡
‹‹እዚህ ቁጭ በይ›› አላት ፖሊሱ፡፡ማርጋሬት ተቀመጠች
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
...ካለ ሽማግሌ ፈቃድ የተወለደ ግን እንደ እርኩስ ስለሚቈጠር የማደግ ዕድል አያገኝም" የማስወረድ ዘዴውም ልምድ ያላቸው ሰዎች በማኅፀን ውስጥ ያለውን ፅንስ ጭንቅላት ከውጭ በኩል በመዳሰስ ሲያገኙ ጭንቅላቱን በሁለት አውራ ጣታቸው ውስጥ ደጋግመው በመጭመቅ..» ሲል ካርለት ፊቷ በስሎ የተበላሸ ቲማቲም መሰለ፣ ከንፈሮቿ ተንገረበቡ፣ መላ አካሏ ራደ"
ከሎ ግን ንግግሩን ቀጠለ፣ «...እድታስወርድ ይደረጋልI ከተወለደም ሕፃኑ ጫካ ይጣላል። ስለዚህ አንድ የሐመር ሴት በሽማግሎች ፈቃድ ማርገዟ ከታወቀ በኋላ ከባሏ ጋር ግንኙነት ሳታደርግ ፅንሱ አድጎ መውለጃዋ ሲደርስና ምጥ ቢይዛት በአካባቢዋ የሚኖሩ
ሴቶች ይሰበሰቡና እጅና እግሯን ጥፍር አድርገው ይዘው፣ አፍዋን ያፍኗታል" ይህም ልጁ የእናቱን ማኅፀን ለቆ ተፈትልኮ
እንዲወጣ ይረዳል» ሲል ካርለት ፍርሃት መላ አካሏን አንገጫገጨው። እሷም እንደታፈነች ሁሉ ልቧ ዘለለባት።
«ውልጃ ባፈና? በምጥ ላይ ሌላ ምጥ? » ከሎ ግን ጨዋታውን ቀጠለ።
«እንግዲህ እንደ ነገሩ ታርሳ ራቁቱን ለተወለደው ሕፃን መታቀፊያ፣ ፎጣ፣ ሙቀት፣ ጂኒ ጃንካ ሳያስፈልገው የቡና ውኃ በማጠጣት
አቀባበል ይደረግለታል። ልጁ ቁሩንና ሙቀቱን ተቋቁሞ አደግ እያለ
ሲመጣ ግን እናቱ ከማማጡ በላይ ትጨነቃለች አባትም ውስጥ
ለውስጥ ይሳቀቃል።
የሚጮኸው ጅብ ሆድ ዕቃዋን፣ የከሎ ወሬ ደግሞ ሕሊናዋ አተረማመሰባት። ትሰማዋለችI የምትሰማው ግን ለማወቅ ሳይሆን
በቃ ከአቅሜ በላይ የሆነ ‹አስፈሪ ነው ብላ መናገር ተስኗት ነው ደንታ ቢሱ ከሎ ግን ጨዋታውን ቀጠለ"
«በሐመር ማኅበረሰብ ላም፣ በሬ፣ በግ...ጥርስ የሚያበቅሉት በታችኛው ድዳቸው ስለሆነ ‹ቅዱስ› ሲባሉ አህያ፣ ፈረስ፣ ጅብ...
ጥርስ የሚያበቅሉት በላይኛው ድዳቸው በመሆኑ እርኩስ ይባላሉ"
የሰው ልጅም የመጀመሪያውን (የወተት ጥርስ ማብቀል የሚገባው
እንደ ቅዱሳን እንስሳት በታችኛው ድዱ መሆን ሲኖርበት፣ እንደ እርኩሳን እንስሳት በላይኛው ድዱ ካበቀለ ከእርኩሳን እንስሳት እንደ አንዱ ስለሚቆጠር ለማኅበረሰቡ አይበጅም ቢያድግም አባቱ
የሚጋፋ፣ የሚገድል፣ የሚበጠብጥ ስለሚሆን ገፊ ወይንም በአካባቢው አጠራር «ሚንጊ» ተብሉ ይጣላል።
«ጥርስ እንደማብቀሉ ሁሉ መውለቁ ላይም በቅድሚያ መውለቅ የሚገባው በታችኛው ድድ የበቀለው ጥርስ መሆን ሲገባው፣
በላይኛው ድዱ የበቀለው ጥርስ ቀድሞ ከወለቀ ሚንጊ ነው ተብሎ
አሁንም ይጣላል ከዚህ በተጨማሪም፣ ሕፃኑ የታችኛው ጥርሱ ከመውለቁ በፊት በአጋጣሚ እንኳ ወድቆ ወይንም በሌላ መንገድ
የላይኛው ጥርሱ ቢወልቅ ሚንጊ ተብሎ ከማኅበረሰቡ እንዲወገድ ይደረጋል» ከሎ ሆራ «ኢ ህ አለና፣
«እና እኔም እንደነገርኩሽ ሚንጊ ነኝ» አላት"
«ታዲያ አንተ ‹ሚንጊ ነህ› ተብለህ ተጥለህ ነበር?» ካርለት፣ ካለማብራሪያ መልሱን በአሉታ ወይንም በአወንታ እንዲመልስላት
በሕሊናዋ እየተማጸነች ጠየቀችው"
«አዎ!» ብሎ፣ ጭንቅላቱንና ትከሻው ላይ በጦር የተወጋውንና በድንጋይ የተፈነከተውን አሳያት" ከዚያ ቀና ብሎ ጨለማውንና
ከዋክብቱን ተመለከተና እንዴት አድርገው እንደ ጣሉት ጨዋታውን
ሲቀጥል ካርለት በሕሊናዋ «ከሎ ለእኔም የሚያዝን አንጀት ይኑርህ እንጂ» በማለት፣ እየተብሰከሰከች የማይቀርላትን ጨዋታ ለመስማት ጉንጯን በጣቶቿ ደግፋ፣ ዓይኖቿን በማፍጠጥ ዓይን ዓይኑን
ተመለከተችው"
«እኔ የተወለድኩት ሐመሮች ተሰባሰቡበት ከሚባለው የቡስካ ተራራ ስር ላላ ከተባለው መንደር ነው" እናቴ በንቲ ኃይሎ ትባላለች" አባቴ ደግሞ ሆራ ሸላ ይባላል። እናቴ ለአባቴ አምስተኛ ሚስት ስትሆን፣ አምስት ልጆችም ወልዳለታለች" እናቴ፣ በልጅነቴ ሁል ጊዜ በምትለብሰው ቆዳ ሸፈን አድርጋ ከሰውነቷ ጋር ትለጥፈኝና ስቅስቅ ብላ ስታለቅስ ቆይታ፣ «ጨዋንዛ» በሚባል ሸካራ ቅጠል
ጥርሴን ትሞርድልኝ ነበር" በወቅቱ ባይገባኝም ኋላ ኋላ ግን የተጣልሁበትን ምክንያት ስሰማ የጥርስ አበቃቀሌ በትክክለኛው መንገድ ማለትም መጀመሪያ በታችኛው ድዴ፣ ቀጥሎ በላይኛው ድዴ ነበር አሉ የበቀለው" ይሁን እንጂ፣ አንድ ጊዜ ጥጃ
ለመመለስ ስሮጥ ወድቄ የላይኛው ጥርሴ አንዱ ወለቀ፣ አንደኛው
ተሸረፈ። እንዳበቃቀሉ ሁሉ፣ በቅድሚያ የታችኛው ድዴ ላይ የበቀለው ጥርስ መውለቅ ሲገባው፣ የላይኛው ጥርሴ ቀድሞ
በመውለቁ፣ ለአደጋ ተጋለጥሁ" እናቴ፣ በሸካራው የጨዋንዛ ቅጠል
ጥርሴን ስትሞርድልኝ የነበረው ለካ የታችኛው ድዴ ጥርስ ቀድሞ የወለቀ ለማስመሰል ኖሯል"
«ይሁን እንጂ፣ ጥረቷ ከንቱ ነበር" ወድቄ ሳለቅስና ጥርሴ ወልቆ ያዩኝ ሰዎች ለሽማግሎች መንገራቸው አይቀሬ ነበር" እናም አንድ
ቀን አባቴ ባልነበረበት ወቅት፣ ሚንጊ የተባሉ ልጆችን የሚጥሉ
ሽማግሎች ወደ እኛ ጎጆ መጡ" እናቴ፣ ከርቀት እንዳየቻቸው ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ሰውነቴን እንቦሳዋን እንደምትልስ ላም እየሳመችና እየላሰች አለቀሰች።
«ከእናቴ ጋር በተለያየ አጋጣሚ እንለያይ ነበር ከብቶች በድርቅ ጊዜ እርቀው ሲሄዱ፣ ወደ ማሳ፣ ለገበያ ወዘተ.ስትሄድ ሁለትና ሦስት ቀናት፣ አልፎ አልፎ ደግሞ ከዚያም በላይ እንለያያለን ታዲያ ስንለያይ እናቴ ታለቅሳለች እኔ ግን የእሷ ሁኔታ ቢረብሸኝም
ተሎ ወደ ጨዋታዬ እመለስ ነበር። የዛን ቀን ሽማግሎች፣ «ጥርሱ
አስወልቀን እናምጣው» ብለው፣ በጠንካራው እጃቸው ትንሿን እጄን በጨመቁ ቁጥር ግን እንባዬ ሳያቋርጥ ይንዠቀዠቅ ነበር"
«እናቴ ሽማግሎች ጥርሱን አስወልቀን እናምጣው ብለው ሲጠይቋት ካለምንም ተቃውሞ ገፋ አድርጋ አሳልፋ ብትሰጠኝም! ትከሻዋን በሁለት እጆቿ አቅፋ፣ ድምፅዋን አጥፍታ፣ አምርራ
ስታለቅስ ለአደገኛ ሁኔታ እንደተጋለጥኩ ገመትሁ" ሆኖም ግን ምን እንደሚደርስብኝና ለምንስ እንደምቀጣ አላወቅሁም ነበር"
«ሁለቱ ሰዎች ከመንደራችን እያራቁ ሲወስዱኝ እናቴ እጇ
እያርገበገበች ስታለቅስ ትታየኝ ነበር። እንዲያውም እስከ አሁን ድረስ እንኳ ሰው እንደ እሷ ስፍስፍ ብሎ ሲያለቅስ አይቼ
አላውቅም"
«ከመንደራችን ብዙ ርቀን ወደ ጫካው ውስጥ እስክንገባ ሽማግሎች ምንም ሳያወሩኝ ሄድንና የሆነ ገደል አጠገብ ስንደርስ ከፊለፊታቸው ወደነሱ ሳልዞር እንድቆም ነገሩኝ" እኔ ግን፣ ያሉኝን
ለመፈጸም ስላልተቻለኝ ዘወር ስል፣ አንደኛው ሽማግሌ ጦሩን ወደ
ትከሻዬ ሲሰድ ተመለከትኩኝ" ከዚያ በኋላ ሰውነቴን ሲወጋኝና
ለመጮህ ስሞክር፣ ገፍትረው ወደ ገደሉ ከተቱኝ ገደሉ ውስጥ የነበረው ድንጋይ ደግሞ እራሴን ተረተረኝ፤ ደም ፊቴን አለበሰው የሞት ሞቴን ግን የእናቴን፣ የወንድሜን፣ የአባቴን...ስም እየጠራሁ
ጮሁኩ" የደረሰልኝ ግን አልነበረም።
«ስለዚህ፣ ጉድጓድ ውስጥ እንደሆንኩ ስጓጉር ውዬ አድሬ፣ ጠዋት ላይ ድምፄ ተዘጋ። ረፈድፈድ ሲል የሰው ድምፅ ሰማሁ"
የሰማሁት ድምፅ ግን የሰው ቢሆንም ቋንቋው የማውቀው ሐመርኛ
አልነበረም" ለመጣራት ብሞክርም ድምፄ እምቢ አለኝ።
«የአጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ፣ አንዷ በልቅሶ የተዘጋውን ድምፄን ሰምታ ኖሮ፣ አብረዋት ከሐመር ቆቄ ከተማ የመጡትን ሴቶች ጠርታ በድንጋጤ ተያይዘው ሄዱ መሰለኝ ድምፃቸው ጠፋብኝ" ብዙ ቆይቼ
ግን፣ እንደገና የወንዶችና ሴቶች ድምፅ ተሰማኝ ከወላጆቼ ጋር ሳለሁ፣ እነዚያን መሳይ ሰዎች ወደ መንደራችን ሲመጡ፣ በፍርሃት ፈርጥጬ እሮጥ ነበር" ሆኖም ግን፣ የማልፈራቸው የኔ ወገኖች
ስለጨከኑብኝ መሰለኝ፣ አለባበሳቸውንና ቋንቋቸውን የማላውቃቸው ሰዎች ከጉድጓድ ውስጥ አውጥተው የሚበላ ሲሰጡኝና ሲያሳክ
ሙኝ፣ አንድም ተቃውሞ አላሰማሁም"
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
...ካለ ሽማግሌ ፈቃድ የተወለደ ግን እንደ እርኩስ ስለሚቈጠር የማደግ ዕድል አያገኝም" የማስወረድ ዘዴውም ልምድ ያላቸው ሰዎች በማኅፀን ውስጥ ያለውን ፅንስ ጭንቅላት ከውጭ በኩል በመዳሰስ ሲያገኙ ጭንቅላቱን በሁለት አውራ ጣታቸው ውስጥ ደጋግመው በመጭመቅ..» ሲል ካርለት ፊቷ በስሎ የተበላሸ ቲማቲም መሰለ፣ ከንፈሮቿ ተንገረበቡ፣ መላ አካሏ ራደ"
ከሎ ግን ንግግሩን ቀጠለ፣ «...እድታስወርድ ይደረጋልI ከተወለደም ሕፃኑ ጫካ ይጣላል። ስለዚህ አንድ የሐመር ሴት በሽማግሎች ፈቃድ ማርገዟ ከታወቀ በኋላ ከባሏ ጋር ግንኙነት ሳታደርግ ፅንሱ አድጎ መውለጃዋ ሲደርስና ምጥ ቢይዛት በአካባቢዋ የሚኖሩ
ሴቶች ይሰበሰቡና እጅና እግሯን ጥፍር አድርገው ይዘው፣ አፍዋን ያፍኗታል" ይህም ልጁ የእናቱን ማኅፀን ለቆ ተፈትልኮ
እንዲወጣ ይረዳል» ሲል ካርለት ፍርሃት መላ አካሏን አንገጫገጨው። እሷም እንደታፈነች ሁሉ ልቧ ዘለለባት።
«ውልጃ ባፈና? በምጥ ላይ ሌላ ምጥ? » ከሎ ግን ጨዋታውን ቀጠለ።
«እንግዲህ እንደ ነገሩ ታርሳ ራቁቱን ለተወለደው ሕፃን መታቀፊያ፣ ፎጣ፣ ሙቀት፣ ጂኒ ጃንካ ሳያስፈልገው የቡና ውኃ በማጠጣት
አቀባበል ይደረግለታል። ልጁ ቁሩንና ሙቀቱን ተቋቁሞ አደግ እያለ
ሲመጣ ግን እናቱ ከማማጡ በላይ ትጨነቃለች አባትም ውስጥ
ለውስጥ ይሳቀቃል።
የሚጮኸው ጅብ ሆድ ዕቃዋን፣ የከሎ ወሬ ደግሞ ሕሊናዋ አተረማመሰባት። ትሰማዋለችI የምትሰማው ግን ለማወቅ ሳይሆን
በቃ ከአቅሜ በላይ የሆነ ‹አስፈሪ ነው ብላ መናገር ተስኗት ነው ደንታ ቢሱ ከሎ ግን ጨዋታውን ቀጠለ"
«በሐመር ማኅበረሰብ ላም፣ በሬ፣ በግ...ጥርስ የሚያበቅሉት በታችኛው ድዳቸው ስለሆነ ‹ቅዱስ› ሲባሉ አህያ፣ ፈረስ፣ ጅብ...
ጥርስ የሚያበቅሉት በላይኛው ድዳቸው በመሆኑ እርኩስ ይባላሉ"
የሰው ልጅም የመጀመሪያውን (የወተት ጥርስ ማብቀል የሚገባው
እንደ ቅዱሳን እንስሳት በታችኛው ድዱ መሆን ሲኖርበት፣ እንደ እርኩሳን እንስሳት በላይኛው ድዱ ካበቀለ ከእርኩሳን እንስሳት እንደ አንዱ ስለሚቆጠር ለማኅበረሰቡ አይበጅም ቢያድግም አባቱ
የሚጋፋ፣ የሚገድል፣ የሚበጠብጥ ስለሚሆን ገፊ ወይንም በአካባቢው አጠራር «ሚንጊ» ተብሉ ይጣላል።
«ጥርስ እንደማብቀሉ ሁሉ መውለቁ ላይም በቅድሚያ መውለቅ የሚገባው በታችኛው ድድ የበቀለው ጥርስ መሆን ሲገባው፣
በላይኛው ድዱ የበቀለው ጥርስ ቀድሞ ከወለቀ ሚንጊ ነው ተብሎ
አሁንም ይጣላል ከዚህ በተጨማሪም፣ ሕፃኑ የታችኛው ጥርሱ ከመውለቁ በፊት በአጋጣሚ እንኳ ወድቆ ወይንም በሌላ መንገድ
የላይኛው ጥርሱ ቢወልቅ ሚንጊ ተብሎ ከማኅበረሰቡ እንዲወገድ ይደረጋል» ከሎ ሆራ «ኢ ህ አለና፣
«እና እኔም እንደነገርኩሽ ሚንጊ ነኝ» አላት"
«ታዲያ አንተ ‹ሚንጊ ነህ› ተብለህ ተጥለህ ነበር?» ካርለት፣ ካለማብራሪያ መልሱን በአሉታ ወይንም በአወንታ እንዲመልስላት
በሕሊናዋ እየተማጸነች ጠየቀችው"
«አዎ!» ብሎ፣ ጭንቅላቱንና ትከሻው ላይ በጦር የተወጋውንና በድንጋይ የተፈነከተውን አሳያት" ከዚያ ቀና ብሎ ጨለማውንና
ከዋክብቱን ተመለከተና እንዴት አድርገው እንደ ጣሉት ጨዋታውን
ሲቀጥል ካርለት በሕሊናዋ «ከሎ ለእኔም የሚያዝን አንጀት ይኑርህ እንጂ» በማለት፣ እየተብሰከሰከች የማይቀርላትን ጨዋታ ለመስማት ጉንጯን በጣቶቿ ደግፋ፣ ዓይኖቿን በማፍጠጥ ዓይን ዓይኑን
ተመለከተችው"
«እኔ የተወለድኩት ሐመሮች ተሰባሰቡበት ከሚባለው የቡስካ ተራራ ስር ላላ ከተባለው መንደር ነው" እናቴ በንቲ ኃይሎ ትባላለች" አባቴ ደግሞ ሆራ ሸላ ይባላል። እናቴ ለአባቴ አምስተኛ ሚስት ስትሆን፣ አምስት ልጆችም ወልዳለታለች" እናቴ፣ በልጅነቴ ሁል ጊዜ በምትለብሰው ቆዳ ሸፈን አድርጋ ከሰውነቷ ጋር ትለጥፈኝና ስቅስቅ ብላ ስታለቅስ ቆይታ፣ «ጨዋንዛ» በሚባል ሸካራ ቅጠል
ጥርሴን ትሞርድልኝ ነበር" በወቅቱ ባይገባኝም ኋላ ኋላ ግን የተጣልሁበትን ምክንያት ስሰማ የጥርስ አበቃቀሌ በትክክለኛው መንገድ ማለትም መጀመሪያ በታችኛው ድዴ፣ ቀጥሎ በላይኛው ድዴ ነበር አሉ የበቀለው" ይሁን እንጂ፣ አንድ ጊዜ ጥጃ
ለመመለስ ስሮጥ ወድቄ የላይኛው ጥርሴ አንዱ ወለቀ፣ አንደኛው
ተሸረፈ። እንዳበቃቀሉ ሁሉ፣ በቅድሚያ የታችኛው ድዴ ላይ የበቀለው ጥርስ መውለቅ ሲገባው፣ የላይኛው ጥርሴ ቀድሞ
በመውለቁ፣ ለአደጋ ተጋለጥሁ" እናቴ፣ በሸካራው የጨዋንዛ ቅጠል
ጥርሴን ስትሞርድልኝ የነበረው ለካ የታችኛው ድዴ ጥርስ ቀድሞ የወለቀ ለማስመሰል ኖሯል"
«ይሁን እንጂ፣ ጥረቷ ከንቱ ነበር" ወድቄ ሳለቅስና ጥርሴ ወልቆ ያዩኝ ሰዎች ለሽማግሎች መንገራቸው አይቀሬ ነበር" እናም አንድ
ቀን አባቴ ባልነበረበት ወቅት፣ ሚንጊ የተባሉ ልጆችን የሚጥሉ
ሽማግሎች ወደ እኛ ጎጆ መጡ" እናቴ፣ ከርቀት እንዳየቻቸው ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ ሰውነቴን እንቦሳዋን እንደምትልስ ላም እየሳመችና እየላሰች አለቀሰች።
«ከእናቴ ጋር በተለያየ አጋጣሚ እንለያይ ነበር ከብቶች በድርቅ ጊዜ እርቀው ሲሄዱ፣ ወደ ማሳ፣ ለገበያ ወዘተ.ስትሄድ ሁለትና ሦስት ቀናት፣ አልፎ አልፎ ደግሞ ከዚያም በላይ እንለያያለን ታዲያ ስንለያይ እናቴ ታለቅሳለች እኔ ግን የእሷ ሁኔታ ቢረብሸኝም
ተሎ ወደ ጨዋታዬ እመለስ ነበር። የዛን ቀን ሽማግሎች፣ «ጥርሱ
አስወልቀን እናምጣው» ብለው፣ በጠንካራው እጃቸው ትንሿን እጄን በጨመቁ ቁጥር ግን እንባዬ ሳያቋርጥ ይንዠቀዠቅ ነበር"
«እናቴ ሽማግሎች ጥርሱን አስወልቀን እናምጣው ብለው ሲጠይቋት ካለምንም ተቃውሞ ገፋ አድርጋ አሳልፋ ብትሰጠኝም! ትከሻዋን በሁለት እጆቿ አቅፋ፣ ድምፅዋን አጥፍታ፣ አምርራ
ስታለቅስ ለአደገኛ ሁኔታ እንደተጋለጥኩ ገመትሁ" ሆኖም ግን ምን እንደሚደርስብኝና ለምንስ እንደምቀጣ አላወቅሁም ነበር"
«ሁለቱ ሰዎች ከመንደራችን እያራቁ ሲወስዱኝ እናቴ እጇ
እያርገበገበች ስታለቅስ ትታየኝ ነበር። እንዲያውም እስከ አሁን ድረስ እንኳ ሰው እንደ እሷ ስፍስፍ ብሎ ሲያለቅስ አይቼ
አላውቅም"
«ከመንደራችን ብዙ ርቀን ወደ ጫካው ውስጥ እስክንገባ ሽማግሎች ምንም ሳያወሩኝ ሄድንና የሆነ ገደል አጠገብ ስንደርስ ከፊለፊታቸው ወደነሱ ሳልዞር እንድቆም ነገሩኝ" እኔ ግን፣ ያሉኝን
ለመፈጸም ስላልተቻለኝ ዘወር ስል፣ አንደኛው ሽማግሌ ጦሩን ወደ
ትከሻዬ ሲሰድ ተመለከትኩኝ" ከዚያ በኋላ ሰውነቴን ሲወጋኝና
ለመጮህ ስሞክር፣ ገፍትረው ወደ ገደሉ ከተቱኝ ገደሉ ውስጥ የነበረው ድንጋይ ደግሞ እራሴን ተረተረኝ፤ ደም ፊቴን አለበሰው የሞት ሞቴን ግን የእናቴን፣ የወንድሜን፣ የአባቴን...ስም እየጠራሁ
ጮሁኩ" የደረሰልኝ ግን አልነበረም።
«ስለዚህ፣ ጉድጓድ ውስጥ እንደሆንኩ ስጓጉር ውዬ አድሬ፣ ጠዋት ላይ ድምፄ ተዘጋ። ረፈድፈድ ሲል የሰው ድምፅ ሰማሁ"
የሰማሁት ድምፅ ግን የሰው ቢሆንም ቋንቋው የማውቀው ሐመርኛ
አልነበረም" ለመጣራት ብሞክርም ድምፄ እምቢ አለኝ።
«የአጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ፣ አንዷ በልቅሶ የተዘጋውን ድምፄን ሰምታ ኖሮ፣ አብረዋት ከሐመር ቆቄ ከተማ የመጡትን ሴቶች ጠርታ በድንጋጤ ተያይዘው ሄዱ መሰለኝ ድምፃቸው ጠፋብኝ" ብዙ ቆይቼ
ግን፣ እንደገና የወንዶችና ሴቶች ድምፅ ተሰማኝ ከወላጆቼ ጋር ሳለሁ፣ እነዚያን መሳይ ሰዎች ወደ መንደራችን ሲመጡ፣ በፍርሃት ፈርጥጬ እሮጥ ነበር" ሆኖም ግን፣ የማልፈራቸው የኔ ወገኖች
ስለጨከኑብኝ መሰለኝ፣ አለባበሳቸውንና ቋንቋቸውን የማላውቃቸው ሰዎች ከጉድጓድ ውስጥ አውጥተው የሚበላ ሲሰጡኝና ሲያሳክ
ሙኝ፣ አንድም ተቃውሞ አላሰማሁም"
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ቀፎ ሰቃዮች የመድሃኒት ሥርና ቅጠል ፈላጊዎች...
ለመኝታ የሚጠቀሙበት ማማ ላይ ዳራና ደልቲ ቅጠል ጎዝጉዘው
ቅጠል ተንተርሰው የተፈጥሮ ግዴታቸውን ከተወጡ በኋላ ደልቲ
የወደቀበትን ሳያውቀው አድሮ ከተኛበት ነቃ።
ልጃገረዷ ከደስታዋ ብዛት ይመስላል ማማዋ ላይ ፈገግ እንዳለች ፊቷን ዞራ ተጋድማለች ወገቧ ተሰርጉዶ ዳሌዋ
የለበሰችውን የፍየል ቆዳ ወጥሮታል። እጅዋ ጡቷን ቢጫንም ጡቷ ግን እንደ ችካል እጅዋን ወጥሮ ይዟታል… ደልቲ ተኝቶበት ካደረው ከማማው ስር የንጋት ፀሐይ ተኮስ ስታደርገው ከተኛበት ተነስቶ
ሳዳጎራውን ባጭሩ ጠበቅ አድርጎ አስሮ ላዩ ላይ ዝናሩን እንደ ቀበቶ
ታጠቀበት።
ጉሬዛና ጦጣዎች ከዛፍ ዛፍ እየዘለሉ በቂንጥ
እየተንጨዋለሉ በመቦረቅ እንደ ህፃን ልጅ “የአላየን መሰላችሁ..."እንደሚሉ ሁሉ እያሽካኩ ይቀበጣጥራሉ። 'ፈታይ' የሚባሉት ወፎችም ክንፍና ክንፋቸውን ከአካላቸው ጋር እየጠበጠቡ ከዛፍ ዛፍ
ይበራሉ። ንስርም ሰማዩ ላይ ክንፉን አጠፍ ዘርጋ አጠፍ ዘርጋ ያደርግና አየሩ ላይ ይንሳፈፋል... አረንጓዴ የተላበሱት የግራር የጥድ... ዛፎችም የጠዋቷን የፀሐይ ሙቀት እየከመከሙ ጎንበስ ቀና ይላሉ።
የየአካባቢው ያ የጥንቱ የሐመር ቀዬ! ያ የጥንቱ ባንኪሞሮ በብብትና ብብቱ እበትና ንብ ይዞ የመጀመሪያውን የሐመር እሳት የለኮሰበት ቅዱስ ስፍራ ቡስካ ተራራ ሰው አልባነቱ ዉጦት ሐመሮች ሜዳውን መርጠው በብዛት ቢሸሹትም ከአራስ ቤት
እንደወጣች ሴት ድንቡሽቡሽ ብሎ ያምራል።
ደልቲ ዕጽዋቱን ምድሪቱን ሰማዩን ቁልቁል
የተንጣለለውን የአባቱን አገር... ቃኝቶ ወደ ማማው ጠጋ ብሉ አየ።ማማው ላይ ያች የደም ገንቦ ዳራ ተጋድማለች። የተገጠሙ
አይኖችዋን ጉንጯን ከንፈሯን ሰርጓዳ ወገቧን ዳሌዋን አይቶ ስሜቱ ጎምዥቶ ተወራጭቶ ሊያስቸግረው ከመከጀሉ በፊት ዘወር ማለቱን መርጦ ጉዞ ሊጀምር ሲል ሻካራ እጅ ትከሻውን ያዘው።
ዘወር ብሉ አያት። ልጃገሪዷ ትስቃለች አይኖችዋ ግን
እንደተከደኑ ናቸው። ለጥቂት ጊዜ አይን አይኗን
ሲያይ የሚንቦገቦጉት ትናንሽ አይኖችዋ ተከፈቱ። ልጃገረዷ የደልቲ ጉሮሮ
ምራቁን ሲያንጎራጉጭ ሰማችውና “አያ ደልቲ?" አለችው።
ከዚያ አይኖቹን የሰጎን ላባ የሰካባትን ጴሮ የወገኖቹ ጠላት የሆኑትን ሙርሲዎች ገሉ በአምስት ረድፍ መስመር መስመር
የተበጀበትን ሳንቃ ደረቱንና ፈርጣማ እጆቹን አየችና
“ቦርጆ ኢሜ" አለችው አመሰግናለሁ ለማለት:: በሐመር ባህል ቦርጆ ፈጣሪ እድል የፈጣሪ ሃይል ደህንነት... ሲሆን
የእርካታ በሐመሮች የቀን ተቀን ህይወት የመልካም አጋጣሚ መግለጫ ነው። ስቃይ የተጠናወተው ወይም በሞት የተለየ ቦርጆ
ራቀው፤ እድል ጠመመችበትም ይባላል።
ዳራ ደግማ “አያ ደልቲ" ስትለው በአይኖቹ ወይ አላት እኒያ የወተት አረፋ የመሰሉ ጥርሶችዋን እያሳየችው ፍልቅልቅ
አለችና፡-
“አንተ ጀግና ነህ! ልብህ
የብዙ ልጃገረዶችን ፍቅር
ሊያስተናግድ የሚችል ሜዳ ማዘጋጀት ሲገባው ለምን እንደ ፍየል ግንባር ጠባብና ለአንድ ሰው የተዘጋጀ መውጫ የሌለው ማማ ሆነ አለችው ፊቷን ቅጭም አድርጋ
ጀግናው! ተኩሶ የገደለው! እጄን እንጂ ልቤ ግን ፈሪ
ቢሆን ይሆናላ” ብሎ ትክዝ ብሎ ቆየና “ለነገሩ ምነው ጅል ጥያቄ ጠየቅሽኝ? የማማውን መውጫ አንችስ መች አጣሽው ወጥተሽ
ተጋድመሽበት አይደል!” አላት።
የደም ገንቦዋ ደግማ ደጋግማ በሣቅ ተፍለቀለቀችና “አንተ!
አያ ደልቲ እኔንኮ ስሜን ጠርተህ ወደ ደረትህ አላስጠጋኸኝም።
"ጎይቲ" ብለህ ጎይቲን ያገኘህ መስሎህ ነው እኔን ወደ ጎዳናህ ያስገባኸኝ
እኔ ግን ስቋምጥለት የኖርሁትን መንገድ ሳገኝ ባገኘሁት ቀዳዳ እንደ እባብ እየተሳብሁ እንደ አንበሳ እየዘለለሁ ልብህ ውስጥ
ገባሁ::... ከተኛችበት ብድግ ብላ እንደ ቂብ ዶሮ እያሽካካች አካባቢውን በሣቅ አጥለቀለቀችው: በሐመር ባህል ሴት ልጅ የሣቅ ምንጭ ናታ። ፍልቅልቅ ስትል የተጠማው የhፋው ወንድ ሁሉ
ጥሙን የሚቆርጠው በሷ ፈገግታ ነው!
በዚህ መሐል ማር ጠቋሚ ወፍ አጠገባቸው ካለው ዛፍ ላይ ድንገት አርፋ ላባዋ እየተርገፈገፈ በከፍተኛ ድምፅ ማዜም ጀመረች።
ደልቲ የዛችን ወፍ ድምፅ ያውቀው ነበርና ዞር ብሎ በፈገግታ አያት: ወፏ ግን ጨኸቷን ይበልጥ ጨመረችው።
ደልቲ ወደ ልጃገረዷ ዞሮ “ዳራ?” አላት
"ዬ" አለችው
“ደርሼ መጣሁ ብሏት መሣሪያውን ይዞ ሲንቀሳቀስ ወፏ ከተቀመጠችበ ተነስታ በረረች ተከተላት። እንደገና አርፋ እየተጣራች ጠበቀችው አጠገቧ ሲደርስ ተነስታ በረረች እሱም
ተከተላት ዳራም ወፏን የሚከተለውን ጀግናዋን
በአይኗ ተከተለችው፡ ወፏን እየተከተለ ወደ ጫካው ሲገባ የንብ ድምፅ ሰማ፡
ትልቅ : ግንድ ላይ ንቦች እየዘመሩ ይዟዟራሉ ወፏ ደልቲን እየመራች ወስዳ ንቦች ዘንድ ካደረሰችው በኋላ ፊረሱም ሜዳውም
ይኸው'' ብላ ፀጥ ብላ ዛፏ ላይ አርፋ ብብቷን በማንቁርቷ እየኮለኮለች
ተቀመጠች።
ደረቅ ያለ የዛፍ ቅርንጫፍ ዘነጠፈና ከወገቡ ላይ ጩቤውን አውጥቶ ፋቅ ፋቅ አድርጎ አሾለው: ከዚያ በአይኑ የተቆረጠ ደረቅ
ግንድ ሲያማትር ከሱ በስተቀኝ በኩል ግንዱን አዬና ግንዱን በጩቤው ትንሽ አጎድጉዶ...ደ የጠረበውን እንጨት በቀዳዳው ከለካ በኋላ ጣቶቹን በመዘርጋት በመዳፉ አጥብቆ ይዞ እያሽከረከረ ይሰብቀው ጀመር: ለጥቂት ጊዜ ሲሰብቅ እንደቆየ አንድ ነገር መርሳቱን ትዝ አለው
ደረቅ ሣር ወይም ቅጠል። ሄዶ ለማምጣት ቀና ሲል ዳራ ደረቅ ሳር
ይዛ ከፊት ለፊቱ ድቅን አለች:: ቀና ብሉ በአይኖቹ ሳቀላት: ከዚያ እሷ ሳሩን ወደ ጢሱ ቀረብ አድርጋ ስትይዘው ጢሱ ትጉልጉል አለና ነደደ:: ወዲያው ዳራ የደራረቀውን እንጨት አስግብታ እሳቱን
አያያዘች:
ይህን ጊዜ ደልቲ መሳሪያውን ግንዱ ላይ አስደግፎ ዝናሩንና
ሳዳጎራውን ፈቶ ምልምል ራቁቱን እንደሆነ ዳራ የያዘውን እንጨት
ልትሰጠው ዘወር ስትል ራቁቱን አየችው ወዲያው አይኖችዋ ቁልቁል ሽቅብ እንደገና ቁልቁል ሮጡ። ፈዛ ቆመች አይኖቿን ቡዝዝ አድርጋ አየችው ! አያት ተያዩ ጢሱ ይጤሳል: ንቦቹ
ከርቀት ይዘምራሉ። ወፏ ቸኩላለች ዳራ ከንፈሯ ቀጥቀጥ ያለባት
መሰላትና ሳቅ አለች የሳቱ ግለት ሲሰማት ከነበረችበት ነቃችና ዝቅ ብላ አየችው።
“ትሰጭኝ!" አላት ደልቲ እጆቹን ዘርግቶ ሽቅብ ወደ ንቦቹ እያየ: ፈገግታዋን ሳትቀንስ አቀበለችው ጀግናው እሳቱን እንደያዘ
ዘወር ብሎ ሳያያት ወደ ዛፉ ተገጋ እሳቱ ጠፍቷል። ጢሱ ግን እየጨመረ ነው:
ቀና ብሎ ዛፉን አይቶ በግራ እጁ እሳቱን ይዞ በቀኝ እጁ ወደ ዛፉ ቅርንጫፍ ወጣ ዛፉ ሲንቀሳቀስ የጭሱ ጠረን ሲሸታቸው ንቦች ቁልቁል መጡበት ነደፉት፡ ፊቱ ቅጭም ሲል
ዳራ አየኘው: እንደገና ተስቦ ሌላ ቅርንጫፍ ላይ ወጣ ንቦቹ እሾሃቸውን በሰውነቱ እየሰገሰጉ ተረባረቡበት
ስቃዩን ጥርሉን ነክሶ ችሎፀ ሽቅብ እየተሳበ ወጣ... ጢሱን ወደ ቀፎው ሲያስጠጋው ንቦች ጩኸታቸውን እየጨመሩ ሸሹ የድምፃቸው ቃና ተቀየረ: ኡ ኡ ኡ.." ሲሉ ደልቲ እጁን ወደ
ተፈጥሮዊ የግንድ ቀፎ ከተተ። እጁ የማር ሰፈፍ ይዞ ተመለሰ።
እንደገና ከተተው ከዚያ ሰፈፉን በዳራ የፍሬ መልቀሚያ ሾርቃ
ሞልቶ ወረደ:
ዳራ ደልቲ ከዛፉ እንደወረደ፡ “መቼም አልተረፍህም"
ፈርጠም ብላ ጠየቀችው:
“አዬ አስቀርተውኝ ነበር! እንዲያው የሞት ሞቴን…" አለ።ላመል ያህል ጉንጭና ጉንጩ ጨምድዶ ከንፈሩ ለጠጥ ጥርሉ ብልጭ ብሎ።
አይቀርም ኖሯል። የአንተን እንጃ እንጂ እኔ መቼም ማር
አላማረኝም ስትለው፡-
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ቀፎ ሰቃዮች የመድሃኒት ሥርና ቅጠል ፈላጊዎች...
ለመኝታ የሚጠቀሙበት ማማ ላይ ዳራና ደልቲ ቅጠል ጎዝጉዘው
ቅጠል ተንተርሰው የተፈጥሮ ግዴታቸውን ከተወጡ በኋላ ደልቲ
የወደቀበትን ሳያውቀው አድሮ ከተኛበት ነቃ።
ልጃገረዷ ከደስታዋ ብዛት ይመስላል ማማዋ ላይ ፈገግ እንዳለች ፊቷን ዞራ ተጋድማለች ወገቧ ተሰርጉዶ ዳሌዋ
የለበሰችውን የፍየል ቆዳ ወጥሮታል። እጅዋ ጡቷን ቢጫንም ጡቷ ግን እንደ ችካል እጅዋን ወጥሮ ይዟታል… ደልቲ ተኝቶበት ካደረው ከማማው ስር የንጋት ፀሐይ ተኮስ ስታደርገው ከተኛበት ተነስቶ
ሳዳጎራውን ባጭሩ ጠበቅ አድርጎ አስሮ ላዩ ላይ ዝናሩን እንደ ቀበቶ
ታጠቀበት።
ጉሬዛና ጦጣዎች ከዛፍ ዛፍ እየዘለሉ በቂንጥ
እየተንጨዋለሉ በመቦረቅ እንደ ህፃን ልጅ “የአላየን መሰላችሁ..."እንደሚሉ ሁሉ እያሽካኩ ይቀበጣጥራሉ። 'ፈታይ' የሚባሉት ወፎችም ክንፍና ክንፋቸውን ከአካላቸው ጋር እየጠበጠቡ ከዛፍ ዛፍ
ይበራሉ። ንስርም ሰማዩ ላይ ክንፉን አጠፍ ዘርጋ አጠፍ ዘርጋ ያደርግና አየሩ ላይ ይንሳፈፋል... አረንጓዴ የተላበሱት የግራር የጥድ... ዛፎችም የጠዋቷን የፀሐይ ሙቀት እየከመከሙ ጎንበስ ቀና ይላሉ።
የየአካባቢው ያ የጥንቱ የሐመር ቀዬ! ያ የጥንቱ ባንኪሞሮ በብብትና ብብቱ እበትና ንብ ይዞ የመጀመሪያውን የሐመር እሳት የለኮሰበት ቅዱስ ስፍራ ቡስካ ተራራ ሰው አልባነቱ ዉጦት ሐመሮች ሜዳውን መርጠው በብዛት ቢሸሹትም ከአራስ ቤት
እንደወጣች ሴት ድንቡሽቡሽ ብሎ ያምራል።
ደልቲ ዕጽዋቱን ምድሪቱን ሰማዩን ቁልቁል
የተንጣለለውን የአባቱን አገር... ቃኝቶ ወደ ማማው ጠጋ ብሉ አየ።ማማው ላይ ያች የደም ገንቦ ዳራ ተጋድማለች። የተገጠሙ
አይኖችዋን ጉንጯን ከንፈሯን ሰርጓዳ ወገቧን ዳሌዋን አይቶ ስሜቱ ጎምዥቶ ተወራጭቶ ሊያስቸግረው ከመከጀሉ በፊት ዘወር ማለቱን መርጦ ጉዞ ሊጀምር ሲል ሻካራ እጅ ትከሻውን ያዘው።
ዘወር ብሉ አያት። ልጃገሪዷ ትስቃለች አይኖችዋ ግን
እንደተከደኑ ናቸው። ለጥቂት ጊዜ አይን አይኗን
ሲያይ የሚንቦገቦጉት ትናንሽ አይኖችዋ ተከፈቱ። ልጃገረዷ የደልቲ ጉሮሮ
ምራቁን ሲያንጎራጉጭ ሰማችውና “አያ ደልቲ?" አለችው።
ከዚያ አይኖቹን የሰጎን ላባ የሰካባትን ጴሮ የወገኖቹ ጠላት የሆኑትን ሙርሲዎች ገሉ በአምስት ረድፍ መስመር መስመር
የተበጀበትን ሳንቃ ደረቱንና ፈርጣማ እጆቹን አየችና
“ቦርጆ ኢሜ" አለችው አመሰግናለሁ ለማለት:: በሐመር ባህል ቦርጆ ፈጣሪ እድል የፈጣሪ ሃይል ደህንነት... ሲሆን
የእርካታ በሐመሮች የቀን ተቀን ህይወት የመልካም አጋጣሚ መግለጫ ነው። ስቃይ የተጠናወተው ወይም በሞት የተለየ ቦርጆ
ራቀው፤ እድል ጠመመችበትም ይባላል።
ዳራ ደግማ “አያ ደልቲ" ስትለው በአይኖቹ ወይ አላት እኒያ የወተት አረፋ የመሰሉ ጥርሶችዋን እያሳየችው ፍልቅልቅ
አለችና፡-
“አንተ ጀግና ነህ! ልብህ
የብዙ ልጃገረዶችን ፍቅር
ሊያስተናግድ የሚችል ሜዳ ማዘጋጀት ሲገባው ለምን እንደ ፍየል ግንባር ጠባብና ለአንድ ሰው የተዘጋጀ መውጫ የሌለው ማማ ሆነ አለችው ፊቷን ቅጭም አድርጋ
ጀግናው! ተኩሶ የገደለው! እጄን እንጂ ልቤ ግን ፈሪ
ቢሆን ይሆናላ” ብሎ ትክዝ ብሎ ቆየና “ለነገሩ ምነው ጅል ጥያቄ ጠየቅሽኝ? የማማውን መውጫ አንችስ መች አጣሽው ወጥተሽ
ተጋድመሽበት አይደል!” አላት።
የደም ገንቦዋ ደግማ ደጋግማ በሣቅ ተፍለቀለቀችና “አንተ!
አያ ደልቲ እኔንኮ ስሜን ጠርተህ ወደ ደረትህ አላስጠጋኸኝም።
"ጎይቲ" ብለህ ጎይቲን ያገኘህ መስሎህ ነው እኔን ወደ ጎዳናህ ያስገባኸኝ
እኔ ግን ስቋምጥለት የኖርሁትን መንገድ ሳገኝ ባገኘሁት ቀዳዳ እንደ እባብ እየተሳብሁ እንደ አንበሳ እየዘለለሁ ልብህ ውስጥ
ገባሁ::... ከተኛችበት ብድግ ብላ እንደ ቂብ ዶሮ እያሽካካች አካባቢውን በሣቅ አጥለቀለቀችው: በሐመር ባህል ሴት ልጅ የሣቅ ምንጭ ናታ። ፍልቅልቅ ስትል የተጠማው የhፋው ወንድ ሁሉ
ጥሙን የሚቆርጠው በሷ ፈገግታ ነው!
በዚህ መሐል ማር ጠቋሚ ወፍ አጠገባቸው ካለው ዛፍ ላይ ድንገት አርፋ ላባዋ እየተርገፈገፈ በከፍተኛ ድምፅ ማዜም ጀመረች።
ደልቲ የዛችን ወፍ ድምፅ ያውቀው ነበርና ዞር ብሎ በፈገግታ አያት: ወፏ ግን ጨኸቷን ይበልጥ ጨመረችው።
ደልቲ ወደ ልጃገረዷ ዞሮ “ዳራ?” አላት
"ዬ" አለችው
“ደርሼ መጣሁ ብሏት መሣሪያውን ይዞ ሲንቀሳቀስ ወፏ ከተቀመጠችበ ተነስታ በረረች ተከተላት። እንደገና አርፋ እየተጣራች ጠበቀችው አጠገቧ ሲደርስ ተነስታ በረረች እሱም
ተከተላት ዳራም ወፏን የሚከተለውን ጀግናዋን
በአይኗ ተከተለችው፡ ወፏን እየተከተለ ወደ ጫካው ሲገባ የንብ ድምፅ ሰማ፡
ትልቅ : ግንድ ላይ ንቦች እየዘመሩ ይዟዟራሉ ወፏ ደልቲን እየመራች ወስዳ ንቦች ዘንድ ካደረሰችው በኋላ ፊረሱም ሜዳውም
ይኸው'' ብላ ፀጥ ብላ ዛፏ ላይ አርፋ ብብቷን በማንቁርቷ እየኮለኮለች
ተቀመጠች።
ደረቅ ያለ የዛፍ ቅርንጫፍ ዘነጠፈና ከወገቡ ላይ ጩቤውን አውጥቶ ፋቅ ፋቅ አድርጎ አሾለው: ከዚያ በአይኑ የተቆረጠ ደረቅ
ግንድ ሲያማትር ከሱ በስተቀኝ በኩል ግንዱን አዬና ግንዱን በጩቤው ትንሽ አጎድጉዶ...ደ የጠረበውን እንጨት በቀዳዳው ከለካ በኋላ ጣቶቹን በመዘርጋት በመዳፉ አጥብቆ ይዞ እያሽከረከረ ይሰብቀው ጀመር: ለጥቂት ጊዜ ሲሰብቅ እንደቆየ አንድ ነገር መርሳቱን ትዝ አለው
ደረቅ ሣር ወይም ቅጠል። ሄዶ ለማምጣት ቀና ሲል ዳራ ደረቅ ሳር
ይዛ ከፊት ለፊቱ ድቅን አለች:: ቀና ብሉ በአይኖቹ ሳቀላት: ከዚያ እሷ ሳሩን ወደ ጢሱ ቀረብ አድርጋ ስትይዘው ጢሱ ትጉልጉል አለና ነደደ:: ወዲያው ዳራ የደራረቀውን እንጨት አስግብታ እሳቱን
አያያዘች:
ይህን ጊዜ ደልቲ መሳሪያውን ግንዱ ላይ አስደግፎ ዝናሩንና
ሳዳጎራውን ፈቶ ምልምል ራቁቱን እንደሆነ ዳራ የያዘውን እንጨት
ልትሰጠው ዘወር ስትል ራቁቱን አየችው ወዲያው አይኖችዋ ቁልቁል ሽቅብ እንደገና ቁልቁል ሮጡ። ፈዛ ቆመች አይኖቿን ቡዝዝ አድርጋ አየችው ! አያት ተያዩ ጢሱ ይጤሳል: ንቦቹ
ከርቀት ይዘምራሉ። ወፏ ቸኩላለች ዳራ ከንፈሯ ቀጥቀጥ ያለባት
መሰላትና ሳቅ አለች የሳቱ ግለት ሲሰማት ከነበረችበት ነቃችና ዝቅ ብላ አየችው።
“ትሰጭኝ!" አላት ደልቲ እጆቹን ዘርግቶ ሽቅብ ወደ ንቦቹ እያየ: ፈገግታዋን ሳትቀንስ አቀበለችው ጀግናው እሳቱን እንደያዘ
ዘወር ብሎ ሳያያት ወደ ዛፉ ተገጋ እሳቱ ጠፍቷል። ጢሱ ግን እየጨመረ ነው:
ቀና ብሎ ዛፉን አይቶ በግራ እጁ እሳቱን ይዞ በቀኝ እጁ ወደ ዛፉ ቅርንጫፍ ወጣ ዛፉ ሲንቀሳቀስ የጭሱ ጠረን ሲሸታቸው ንቦች ቁልቁል መጡበት ነደፉት፡ ፊቱ ቅጭም ሲል
ዳራ አየኘው: እንደገና ተስቦ ሌላ ቅርንጫፍ ላይ ወጣ ንቦቹ እሾሃቸውን በሰውነቱ እየሰገሰጉ ተረባረቡበት
ስቃዩን ጥርሉን ነክሶ ችሎፀ ሽቅብ እየተሳበ ወጣ... ጢሱን ወደ ቀፎው ሲያስጠጋው ንቦች ጩኸታቸውን እየጨመሩ ሸሹ የድምፃቸው ቃና ተቀየረ: ኡ ኡ ኡ.." ሲሉ ደልቲ እጁን ወደ
ተፈጥሮዊ የግንድ ቀፎ ከተተ። እጁ የማር ሰፈፍ ይዞ ተመለሰ።
እንደገና ከተተው ከዚያ ሰፈፉን በዳራ የፍሬ መልቀሚያ ሾርቃ
ሞልቶ ወረደ:
ዳራ ደልቲ ከዛፉ እንደወረደ፡ “መቼም አልተረፍህም"
ፈርጠም ብላ ጠየቀችው:
“አዬ አስቀርተውኝ ነበር! እንዲያው የሞት ሞቴን…" አለ።ላመል ያህል ጉንጭና ጉንጩ ጨምድዶ ከንፈሩ ለጠጥ ጥርሉ ብልጭ ብሎ።
አይቀርም ኖሯል። የአንተን እንጃ እንጂ እኔ መቼም ማር
አላማረኝም ስትለው፡-
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
////
አሁን ወደ ቤቴ ልሄድ ወሰንኩና ወደ እሷ ዞርኩ ...እና አሁንም በድጋሜ ከፊል እርቃኗን ስመለከት እርብድብድ አልኩና"አይ በዚህ ሰአት ዘበኞቹ ሰለሚተኙ ግቢውን አይከፍቱልኝ ይሆን እያልኩ እያሰብኩ ነው።››
"ነውእንዴ? ታዲያ እዚህ እደራ!!"ብላ ዘጭ ያለው ሞራሌን መልሳ ሰማይ ሰቀለችው..፡፡እያንቀጠቀጠኝ የነበረው የውስጥ ቅዝቃዜ ከውስጤ እየተወገደ በምትኩ ሙቀት ሲራወጥ ታወቀኝ፡፡
"ይሻላል?"
"አዎ ..ችግር የለውም...፡፡አለችና አንሶላውን እና ብርድ ልብሱን ገልጣ ከውስጥ ገባች...፡፡እኔም በአፌ ምራቅ እየሞላ ጫማዬን ማውለቅ ጀመርኩ፤ ሸሚዜን አወለቅኩ፤ፓክ አውቴንም አልተውኩ አወለቅኩ፤ በመጨረሻ ሱሪዬን አወለቅኩና ልክ እንደእሷ በፓንት ብቻ ወደ አልጋ ላይ እየተስገበገብኩ ወጣሁ።..እያየኋት ብርድልብሱን ወደእኔ ገፋችና በአንሶላና አልጋልብሱ ተጠቅልላ አንደኛውን ጠርዝ ይዛ ተኛች ..
"ብርድልብሱን ልበስ..ደህና እደር"ብላኝ መብራቱን አጠፋችና ለሽ...፡፡
"እንደተባልኩት በብርድ ልብሱ እርቃኔን ጠቅልዬ ለመተኛት ሞከርኩ...፡፡ምን አይነቱ እንከፍ ነኝ እስኪ ደህና እደር እንዳለችኝ ያልሆነ ነገር ከምቀባጥር በክብር ፈጠን ብዬ ይሄን ክፍል ለቅቄ ብወጣስ?...እሷ እያንኮራፍች ነው፤እኔ ግን ..?እኔማ በሁለት እጇቼ እንትኔን አፍኜ ይዤ እየተገለባጥኩ ነው።በግድ ጉብ ልበልባት ይሆን ?አይ ይሄ አይሆንም ጓደኞቼ በፓለቲካ ምክንያት ታስረው ጀግና ሲባሉ እኔ በአስገድዶ ደፈራ ሀያ አመት ....አይ መታገስ መልካም ነው፡፡እኔ ደግሞ በትግስት አልታማም ..በእፅዋት ሳይንስ ከሀረማያ በዲግሪ ተመርቄ አዲስአበባ ላይ በአስተናጋጅነት ተቀጥሬ በመስራት ኑሮዬን እየገፋሁ ያለው ትሁት ትዕግስተኛ። ከዚህ በላይ ትግስት ምን አለ...?በተወለድኩባት አዲስአበባ ከተማ በተማርኩበት ሞያ ስራ ለማግኘት ከአመት በላይ በየመስሪያ ቤቱ ተንከራተትኩ ..ምንም ጠብ ያለልኝ ነገር የለም...አንድ መስሪያ ቤት ጋምቤላ ልላክህ ይላል...ሌላው ጋ ስሄድ የበጋ ስንዴ ፕሮጀክት አርሲ ላይ አለን እዛ እንላክህ ይለኛል።"ምነው ውትድርና የሰለጠንኩ መሠላቸሁ እንዴ? "ብዬ በእነሱ ይሁን በራሴ እያላገጥኩ አላውቅም ሁሉንም እርግፍ አድርጌ ያለሞያዬ ስባክን ይሄው ይሄን የመሠለ ፈተና…..
የባጥ የቆጡን ሳስብ ምንጊዜ እንቅልፍ እንደወሰደኝ አላውቅም፡፡ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስደኝ፡፡ ….....የበር መንኳኳት ነበር ከእንቅልፍ አለም መዞ ያወጣኝ
‹‹...ማነው? ምንድነው ?››በርግጌ ተነሳው፡፡
"ፅዳት ነው ሰዓት ደርሷል"
"ፅዳት "ዙሪያ ገባውን ቀኘሁ፡፡ነግቷል፡፡ክፍሉ ባዶ ነው.፡፡.ልጅቷ የለችም...፡፡ልብሷቾም ሆነ ዕቃዋቾ የሉም...፡፡ጠረኗ ብቻ ነው ያለው...፡፡ሄዳለች ማለት ነው..፡፡.ምኑ እንክርፍፍ ነገር ነኝ በፈጣሪ...?ምን አለ በጥዋት ተነስቼ ቢያንስ ለመጨረሻ ጊዜ እነዛን አይኗቾን ማለቴ መቀመጫዋን አይቼ በተሰናበትኳት...፡፡በንዴት ከላዬ ላይ ብርድ ልብሱን አሽቀንጥሬ ከላዬ ላይ ወረወርኩ፡፡ ...ከአልጋው ወረድኩ… ጠረጴዛ ላይ ያለውን ልብሴን ሳነሳ የሆኑ ባለመቶ ብር ድፍን ብሮች እና ብጣሽ ወረቀት ድብ ብሎ ወለል ላይ ወደቀ...ብሩን ተውኩና ወረቀቱን አነሳሁት አነበብኩት።
‹‹ደህና ሁን ቆንጇ...ቁርስ በእኔ ነው"ይላል ...
ብሩን አነሳሁና ቆጠርኩት 500 ብር ነው፡፡
‹‹እኔን ብሎ ቆንጆ›› አልኩና በቅጡ እንኳን ልብሴን አስተካክዬ ሳለብስ በንዴት ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
ከውስጤ እየተንቀለቀለ ያለው ንዴት በቀላሉ ሊበርድልኝ ስላልቻለ እቤቴ ስደርስ እንኳን የበራፍ አከፋፈቴና አዘጋጌ ኃይል የተቀላቀለበት ነበር ፡፡
‹‹አንተ ቀልማዳ….››
‹‹አቤት አያቴ››
‹‹የትአባህ ነው ያደርከው…?ሰው ያስባል አትልም እንዴ…?ከአሁን አሁን መጣ እያልኩ ቁጭ ብዬ እኮ ነው ያደርኩት››
‹‹ውይ በጣም ይቅርታ ..ጋሼ ስራ አዞኝ እስከ 9 ሰዓት ስሰራ ስለነበር ደከመኝና እዛው ተኛሁ፡፡››
‹‹እና ሮጥ ብለህ አንድ አፍታ መጥተህ ላድር ነው ብትል የትኛውን ድንበር ስታቆርጥ ነው››ጠንከር ባለ የንዴት ቃና ሲቆጡኝ እንባዬ በአይኔ ሞላ ..ተበሳጫቼ አይደለም..፡፡ይሄን ያህል የሚያስብልኝ ሰው ይኖረል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበረ…፡፡
‹ሁለተኛ አይለመደኝም››ቃል ገባሁ፡፡
‹ፍፅምዐእንዳይለመድህ .
ትደግመውናትጣላኛለህ
.በል አሁን እንደደካከመህ ድምፅህ ያስታውቃል ትንሽ ተኛ፡፡››
‹‹እሺ አያቴ›አልኩና አልጋዬ ላይ ተዘረርኩ፡፡
‹‹ዜና ወርቅ… ›
›.‹‹የዜናወርቅ አዎ እንደዛ ብላ ነበር ስሟን የነገረችኝ…ለዛም ይመስለኛል የዜናወርቅ የሚለው ስም ከእምሮዬ ሞልቶ እየፈሰሰ ያለው….
‹‹ወይ ጉድ ፍቅር ስለሚለው ቃል እራሱ ያሰብኩት ከስንት ጊዜ በኃላ መሆኑ ነው…?አዎ ከስድስት ረጂም አመት በኃላ …፡፡ ፍቅርን እርም ብዬ ነበር…፡፡ልክ እየደጋገሙ እየተንበገበገ ባለ እሳት እጣቱን ከተው እስኪቆስልና ቆዳወ እስኪገሸለጥ ድረስ እያቃጠሉ እንዳስፈራሩት ልጅ አይነት ነበርኩ፡፡.አዎ ፍቅርን የምፈራው ልክ ያ ህፃን ልጅ እድሜ ልኩን እሳትን በሚፈራበት መጠን ነው፡፡እና ጊዜያዊ ስሜቴን ማስወገድ አለብኝ.››.አስቤ አስቤ ሲደክመኝ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡
‹‹ወይ ዝም ብዬህ ቻው እንኳን ሳልልህ ሄድኩ አይደል?››
‹‹አዎ…ግራ አጋባሺኝ እኮ››
‹‹አይ አስቸኮይ ነገር ስላጋጠመኝ ነው .ይቅርታ››
‹‹አይ ምንም አይደል…ግን እቤቴን ማን አሳየሽ? ››
‹‹አለቃህ…ማለቴ የሆቴሉ ባለቤት ለመነኩትና ከአንድ ጩጬ ጋ ላከኝ፡፡››
‹‹እሺ የቤቱን በራፍስ ማን ከፈተልሽ...?እኔ ተኝቼ ነበር››
‹እሱን ተወው .በመምጣቴ አልተደሰትክም እንዴ?››
‹‹አረ በጣም ተደስቼያለሁ…ነገሮች ድንገተኛ ስለሆኑብኝ ግራ ተጋብቼ ነው››
‹እንደዛ ከሆነ እቀፈኝ››
‹‹እሺ…ይሄው….ወደራሴ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት…››
‹‹እዬብዬ.›በተሰባበረ እና በሚያቃትት ድምፅ ጠራችኝ፡፡
‹‹ወዬ ዜናዬ.››
‹በጣም ሞቀኝ…ልብሴን ላውልቅ››
‹አዎ አውልቂ…. እንደውም እኔም ላውልቅ.››አልኩና እኩል እየተረዳዳን ልብሳችንን አወለቅንና እርቃናችንን ተመልሰን እቅፍቅፍ ብለን ተጋደምን….፡፡እርቃናችን ሲፋተግ እሳት ፈጠረ..ነደድኩ… ከንፈሯ ላይ ተጣበቅኩባት…ጭኗን ፈለቀቅኩና ሰርስሬ ከመሀል ገባሁ….ቃተተች…‹‹ወይ የእኔ ጀግና ጎዳኸኝ….ቀስ በል..አመመኝ›››
በእጆቼ አፏን አፈንኳት..እንደዛ ያደረኩት የዜናወርቅን የመቃተት ጩኸት አያቴ እንዳይሰሙንና እንዳይረበሹ ስለፈራሁ ነው፡፡እንኳን እንዲህ የምትቃትት ሴት ይቅርና ጮክ ብሎ የሚያወራ ወንድ ጓደኛ እዚህ ቤት ይዤ መጥቼ አላውቅም፡ተጨነቅኩ፡፡ ስላፈንኳት እሷ ተንፈራገጠች…፡፡ግራ ገባኝ፤ ልልቀቃትና መጮኸን ትቀጥል ወይስ እንዳፈንኳት ልቀጥል …?ብትሞትብኝስ..?፡፡ከመጨነቄ የተነሳ ላቤ መንጠባጠብ ጀመረ …ተስፈንጥሬ ከመኝታዬ ተነሳሁ፤መኝታዬ ባዶ ክፍሉም ኦና ነበር…ዜናወርቅ ሀሳብ ብቻ ነበረች.፡፡ምኞት የፈጠራት ህልም››
‹‹ተመስገን›አልኩ፡፡
‹‹ተመስገን ያልኩት ዜናወርቅ ቤቴ ስላልመጣችና ስላልተዋሰብን ተደስቼ አይደለም..ይልቁንስ የእውነት ሆኖ ጋሽ ሙሉአለም ስላረበሽኳቸውና ስላላስቀየምኳቸው ተደስቼ ነው ተመስጌን ማለቴ..አንዳንዴ ግን ህልም ባይኖር በምኞታችን እና በምናገኘው ነገር መካከል ያለውን ክፍተት በምን እንሞላው ነበር?››
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
////
አሁን ወደ ቤቴ ልሄድ ወሰንኩና ወደ እሷ ዞርኩ ...እና አሁንም በድጋሜ ከፊል እርቃኗን ስመለከት እርብድብድ አልኩና"አይ በዚህ ሰአት ዘበኞቹ ሰለሚተኙ ግቢውን አይከፍቱልኝ ይሆን እያልኩ እያሰብኩ ነው።››
"ነውእንዴ? ታዲያ እዚህ እደራ!!"ብላ ዘጭ ያለው ሞራሌን መልሳ ሰማይ ሰቀለችው..፡፡እያንቀጠቀጠኝ የነበረው የውስጥ ቅዝቃዜ ከውስጤ እየተወገደ በምትኩ ሙቀት ሲራወጥ ታወቀኝ፡፡
"ይሻላል?"
"አዎ ..ችግር የለውም...፡፡አለችና አንሶላውን እና ብርድ ልብሱን ገልጣ ከውስጥ ገባች...፡፡እኔም በአፌ ምራቅ እየሞላ ጫማዬን ማውለቅ ጀመርኩ፤ ሸሚዜን አወለቅኩ፤ፓክ አውቴንም አልተውኩ አወለቅኩ፤ በመጨረሻ ሱሪዬን አወለቅኩና ልክ እንደእሷ በፓንት ብቻ ወደ አልጋ ላይ እየተስገበገብኩ ወጣሁ።..እያየኋት ብርድልብሱን ወደእኔ ገፋችና በአንሶላና አልጋልብሱ ተጠቅልላ አንደኛውን ጠርዝ ይዛ ተኛች ..
"ብርድልብሱን ልበስ..ደህና እደር"ብላኝ መብራቱን አጠፋችና ለሽ...፡፡
"እንደተባልኩት በብርድ ልብሱ እርቃኔን ጠቅልዬ ለመተኛት ሞከርኩ...፡፡ምን አይነቱ እንከፍ ነኝ እስኪ ደህና እደር እንዳለችኝ ያልሆነ ነገር ከምቀባጥር በክብር ፈጠን ብዬ ይሄን ክፍል ለቅቄ ብወጣስ?...እሷ እያንኮራፍች ነው፤እኔ ግን ..?እኔማ በሁለት እጇቼ እንትኔን አፍኜ ይዤ እየተገለባጥኩ ነው።በግድ ጉብ ልበልባት ይሆን ?አይ ይሄ አይሆንም ጓደኞቼ በፓለቲካ ምክንያት ታስረው ጀግና ሲባሉ እኔ በአስገድዶ ደፈራ ሀያ አመት ....አይ መታገስ መልካም ነው፡፡እኔ ደግሞ በትግስት አልታማም ..በእፅዋት ሳይንስ ከሀረማያ በዲግሪ ተመርቄ አዲስአበባ ላይ በአስተናጋጅነት ተቀጥሬ በመስራት ኑሮዬን እየገፋሁ ያለው ትሁት ትዕግስተኛ። ከዚህ በላይ ትግስት ምን አለ...?በተወለድኩባት አዲስአበባ ከተማ በተማርኩበት ሞያ ስራ ለማግኘት ከአመት በላይ በየመስሪያ ቤቱ ተንከራተትኩ ..ምንም ጠብ ያለልኝ ነገር የለም...አንድ መስሪያ ቤት ጋምቤላ ልላክህ ይላል...ሌላው ጋ ስሄድ የበጋ ስንዴ ፕሮጀክት አርሲ ላይ አለን እዛ እንላክህ ይለኛል።"ምነው ውትድርና የሰለጠንኩ መሠላቸሁ እንዴ? "ብዬ በእነሱ ይሁን በራሴ እያላገጥኩ አላውቅም ሁሉንም እርግፍ አድርጌ ያለሞያዬ ስባክን ይሄው ይሄን የመሠለ ፈተና…..
የባጥ የቆጡን ሳስብ ምንጊዜ እንቅልፍ እንደወሰደኝ አላውቅም፡፡ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስደኝ፡፡ ….....የበር መንኳኳት ነበር ከእንቅልፍ አለም መዞ ያወጣኝ
‹‹...ማነው? ምንድነው ?››በርግጌ ተነሳው፡፡
"ፅዳት ነው ሰዓት ደርሷል"
"ፅዳት "ዙሪያ ገባውን ቀኘሁ፡፡ነግቷል፡፡ክፍሉ ባዶ ነው.፡፡.ልጅቷ የለችም...፡፡ልብሷቾም ሆነ ዕቃዋቾ የሉም...፡፡ጠረኗ ብቻ ነው ያለው...፡፡ሄዳለች ማለት ነው..፡፡.ምኑ እንክርፍፍ ነገር ነኝ በፈጣሪ...?ምን አለ በጥዋት ተነስቼ ቢያንስ ለመጨረሻ ጊዜ እነዛን አይኗቾን ማለቴ መቀመጫዋን አይቼ በተሰናበትኳት...፡፡በንዴት ከላዬ ላይ ብርድ ልብሱን አሽቀንጥሬ ከላዬ ላይ ወረወርኩ፡፡ ...ከአልጋው ወረድኩ… ጠረጴዛ ላይ ያለውን ልብሴን ሳነሳ የሆኑ ባለመቶ ብር ድፍን ብሮች እና ብጣሽ ወረቀት ድብ ብሎ ወለል ላይ ወደቀ...ብሩን ተውኩና ወረቀቱን አነሳሁት አነበብኩት።
‹‹ደህና ሁን ቆንጇ...ቁርስ በእኔ ነው"ይላል ...
ብሩን አነሳሁና ቆጠርኩት 500 ብር ነው፡፡
‹‹እኔን ብሎ ቆንጆ›› አልኩና በቅጡ እንኳን ልብሴን አስተካክዬ ሳለብስ በንዴት ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ፡፡
ከውስጤ እየተንቀለቀለ ያለው ንዴት በቀላሉ ሊበርድልኝ ስላልቻለ እቤቴ ስደርስ እንኳን የበራፍ አከፋፈቴና አዘጋጌ ኃይል የተቀላቀለበት ነበር ፡፡
‹‹አንተ ቀልማዳ….››
‹‹አቤት አያቴ››
‹‹የትአባህ ነው ያደርከው…?ሰው ያስባል አትልም እንዴ…?ከአሁን አሁን መጣ እያልኩ ቁጭ ብዬ እኮ ነው ያደርኩት››
‹‹ውይ በጣም ይቅርታ ..ጋሼ ስራ አዞኝ እስከ 9 ሰዓት ስሰራ ስለነበር ደከመኝና እዛው ተኛሁ፡፡››
‹‹እና ሮጥ ብለህ አንድ አፍታ መጥተህ ላድር ነው ብትል የትኛውን ድንበር ስታቆርጥ ነው››ጠንከር ባለ የንዴት ቃና ሲቆጡኝ እንባዬ በአይኔ ሞላ ..ተበሳጫቼ አይደለም..፡፡ይሄን ያህል የሚያስብልኝ ሰው ይኖረል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበረ…፡፡
‹ሁለተኛ አይለመደኝም››ቃል ገባሁ፡፡
‹ፍፅምዐእንዳይለመድህ .
ትደግመውናትጣላኛለህ
.በል አሁን እንደደካከመህ ድምፅህ ያስታውቃል ትንሽ ተኛ፡፡››
‹‹እሺ አያቴ›አልኩና አልጋዬ ላይ ተዘረርኩ፡፡
‹‹ዜና ወርቅ… ›
›.‹‹የዜናወርቅ አዎ እንደዛ ብላ ነበር ስሟን የነገረችኝ…ለዛም ይመስለኛል የዜናወርቅ የሚለው ስም ከእምሮዬ ሞልቶ እየፈሰሰ ያለው….
‹‹ወይ ጉድ ፍቅር ስለሚለው ቃል እራሱ ያሰብኩት ከስንት ጊዜ በኃላ መሆኑ ነው…?አዎ ከስድስት ረጂም አመት በኃላ …፡፡ ፍቅርን እርም ብዬ ነበር…፡፡ልክ እየደጋገሙ እየተንበገበገ ባለ እሳት እጣቱን ከተው እስኪቆስልና ቆዳወ እስኪገሸለጥ ድረስ እያቃጠሉ እንዳስፈራሩት ልጅ አይነት ነበርኩ፡፡.አዎ ፍቅርን የምፈራው ልክ ያ ህፃን ልጅ እድሜ ልኩን እሳትን በሚፈራበት መጠን ነው፡፡እና ጊዜያዊ ስሜቴን ማስወገድ አለብኝ.››.አስቤ አስቤ ሲደክመኝ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡
‹‹ወይ ዝም ብዬህ ቻው እንኳን ሳልልህ ሄድኩ አይደል?››
‹‹አዎ…ግራ አጋባሺኝ እኮ››
‹‹አይ አስቸኮይ ነገር ስላጋጠመኝ ነው .ይቅርታ››
‹‹አይ ምንም አይደል…ግን እቤቴን ማን አሳየሽ? ››
‹‹አለቃህ…ማለቴ የሆቴሉ ባለቤት ለመነኩትና ከአንድ ጩጬ ጋ ላከኝ፡፡››
‹‹እሺ የቤቱን በራፍስ ማን ከፈተልሽ...?እኔ ተኝቼ ነበር››
‹እሱን ተወው .በመምጣቴ አልተደሰትክም እንዴ?››
‹‹አረ በጣም ተደስቼያለሁ…ነገሮች ድንገተኛ ስለሆኑብኝ ግራ ተጋብቼ ነው››
‹እንደዛ ከሆነ እቀፈኝ››
‹‹እሺ…ይሄው….ወደራሴ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት…››
‹‹እዬብዬ.›በተሰባበረ እና በሚያቃትት ድምፅ ጠራችኝ፡፡
‹‹ወዬ ዜናዬ.››
‹በጣም ሞቀኝ…ልብሴን ላውልቅ››
‹አዎ አውልቂ…. እንደውም እኔም ላውልቅ.››አልኩና እኩል እየተረዳዳን ልብሳችንን አወለቅንና እርቃናችንን ተመልሰን እቅፍቅፍ ብለን ተጋደምን….፡፡እርቃናችን ሲፋተግ እሳት ፈጠረ..ነደድኩ… ከንፈሯ ላይ ተጣበቅኩባት…ጭኗን ፈለቀቅኩና ሰርስሬ ከመሀል ገባሁ….ቃተተች…‹‹ወይ የእኔ ጀግና ጎዳኸኝ….ቀስ በል..አመመኝ›››
በእጆቼ አፏን አፈንኳት..እንደዛ ያደረኩት የዜናወርቅን የመቃተት ጩኸት አያቴ እንዳይሰሙንና እንዳይረበሹ ስለፈራሁ ነው፡፡እንኳን እንዲህ የምትቃትት ሴት ይቅርና ጮክ ብሎ የሚያወራ ወንድ ጓደኛ እዚህ ቤት ይዤ መጥቼ አላውቅም፡ተጨነቅኩ፡፡ ስላፈንኳት እሷ ተንፈራገጠች…፡፡ግራ ገባኝ፤ ልልቀቃትና መጮኸን ትቀጥል ወይስ እንዳፈንኳት ልቀጥል …?ብትሞትብኝስ..?፡፡ከመጨነቄ የተነሳ ላቤ መንጠባጠብ ጀመረ …ተስፈንጥሬ ከመኝታዬ ተነሳሁ፤መኝታዬ ባዶ ክፍሉም ኦና ነበር…ዜናወርቅ ሀሳብ ብቻ ነበረች.፡፡ምኞት የፈጠራት ህልም››
‹‹ተመስገን›አልኩ፡፡
‹‹ተመስገን ያልኩት ዜናወርቅ ቤቴ ስላልመጣችና ስላልተዋሰብን ተደስቼ አይደለም..ይልቁንስ የእውነት ሆኖ ጋሽ ሙሉአለም ስላረበሽኳቸውና ስላላስቀየምኳቸው ተደስቼ ነው ተመስጌን ማለቴ..አንዳንዴ ግን ህልም ባይኖር በምኞታችን እና በምናገኘው ነገር መካከል ያለውን ክፍተት በምን እንሞላው ነበር?››
✨ይቀጥላል✨
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
ካለወትሮው እያከታተለ የሚወርደው ዝናብ የሐመርን ምድር:
የወሮን መንደር የብርሃን ጥላ አልብሷታል" ሰማዩ ላይ በጨርቅ እንደተጠቀለለ ህፃን ዳመናው እየተገለባበጠ
ምርር ብሎ እየጮኸ
ብልጭታው በሁሉም አቅጣጫ ይፈነጣጠቃል
ከክቧ የሐመሮች ጎጆ የሚትጎለጎለው
ከሚጥመለመለው ጥቁር ዳመና ጋር እየተደባለቀ ይጠፋል ፍየሎች በጎች ጥጆች ገና ከበረታቸው አልወጡም በከብቶች አንገት የተንጠለጠለው የኤሊ ድንጋይ ከብቶቹ በተንቀሳቀሱ ቁጥር
ቋቋ ቋቋ እያለ ይሰማል" መንደሯ ልብ ብለው ሲያዳምጧት ትንፋሽዋ እንደወትሮዋ ነው፤ ማነጠሱ፥ ጨዋታው፥ እንጉርጉሮው: ቀልዱ ወፍጮው፥ የወፎቹ ዝማሬ ሁሉም ከዘመናት በፊት
እንደተቃኘው ነው
የናት ጉያ ሙቀት የናፈቃቸው ሆዳቸውን የሞረሞራቸው ጥጆች ግን ከናታችን አራክቡን በሚል ሆድን በሚያላውስ ቅላፄ እ-
ም--ዋ … እም-ቡ-ዋ እያሉ የጌቶቻቸውን ጆሮና ቀልብ ለመሳብ ረሃብና ናፍቆታቸውን በለሆስታ ዜማ አለዝበው ያንጎራጉራሉ" ላሞች እንደሌሎች ከብቶች ማመንዠካቸውን አቁመው ፊታቸውን ወደ ጥጆቻቸው አዙረው ዐይናቸውን እያቁለጨለጩ: ሳጋቸውን እያሰሙ የጥጆችን ከለላ በአፍንጫቸው እያሸተቱና
እየነካኩ የናትነት አንጀታቸው ረፍት ነስቶ ያንሰፈስፋቸዋል አንተነህ ይመር ከምድጃው ጎን ካለችው ትንሽ መደብ ላይ
በቦርኮታው የቀኝ ጭኑን አስደግፎ፥ ጎኑን እሳቱን እያሞቀ እሱም
የማይሰማ ውስጡ ፈልቶ እዚያው ተኖ የሚቀረውን ሳጉን ራሱ ለራሱ ይሰማል
ባለቤቱ እሳቱን እየቆሰቆሰች ሻላው (ቆጡ) ላይ ባሰረችው ጠፍር የአንጠለጠለችውን እርጎ በቀኝ እጅዋ ወደ ፊትና ኋላ
ትንጣለች ቅቤ ለማውጣት ነጭና ጥቁር መልክ ያለው ቁርበት ከበስተ ኋላዋ ተነጥፏል ዳሚ ሰረቅ እያደረገች ስታየው ቆይታ
"ይእ! ምን ሆነሃል የኔ ጌታ?" አለችው
ቢጨንቃት" እሱ ግን ዝም አላት ዝም እየተነፈሰ ጭጭ
"ተቡኑ ልስጥህ?"
ጋልታምቤ መልስ ሳይሰጣት ውጭውን
አየው በጠባቧ በር በግድግዳው ቀዳዳ አየሩ ክርስስ ያለ ነው ቀዝቃዛ የሱም ልብ ቀዝቅዛለች
በሐመር ባህል የተጠየቀ ሁሉ ወዲያው የመመለስ ግዴታ የለበትም አዋቂ አስተሳሰቡ የበሰለ ከመናገሩ በፊት ልቡን ዐይኑ ላይ ማውጣት አለበት በልቦናው የሚያይ ሐሳቡ ሚዛናዊ ሆነ ክፉና ደግ ለመለየት በቃ ሃላፊነት ለመቀበል ደረሰ ማለት ነው" ጋልታምቤም በዚህ መላ
የሚስቱን ጥያቄና ጭጋጋማውን ቀን በልቦናው አየው" ልቦናው ግን ምንም እንዲል አልፈቀደለትም
ዝምታ ደግሞ በራሱ ቋንቋ ነው ዝምታና ዐይን ዝምታና ጥርስ ዝምታና ዝም በአይነቱ የተለያዬ ትርጉም አላቸው በቢጫው በሬ ምድር በሐመር።
ዳሚ የጋልታምቤን ዝምታና ዐይን አይታ የሚያሳስበው ነገር እንዳለ አውጥቶ ሊነግራት ግን እንዳልፈለገ ተረዳች ያን ጊዜ።
ይእ! ምን ሆነ? እንግዲ ተሱ ይምጣ'ንጂ እኔ ምናባቴ
ላርግለት ብላ እሷም ዝም አለች ዝም ተባባሉ እሱና እሷ እሱና እሱ: እሱና ተፈጥሮ ተዘጋጉ"
ጋልታምቤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሰረቅ አድርጎ አያት ልቧን ከንፈሯ ላይ ተቀምጦ አየው ፍርሃት ነፋ ልትት፤ ነፋ ልትት
ሲያደርገው ሲገፋፋው ሲያንቀጠቅጠው ሲያወዛውዘው ተመለከተው
ዳሚ ከበስተግራዋ ተሰካክተው ከተቀመጡት በጨሌ ያጌጠውን
ሾርቃ አንስታ ጠረግ ጠረግ በማድረግ ከተወዘተው እንስራ በቅል ጭልፋ ሸፈሮ ቡና ቀድታ አቀበለችው
ጋልታምቤ እግሩን አንፈራጦ ተቀበላትና ግራ ቀኝ ፊትና ኋላ ጎለል ጎለል አድርጎ አበረደው ከዚያ እፉት ብሎ ፕስስ አድርጎ አማተበ ሸፈሮ ቡና የቦርጆ ፍሬ ሽፋን ነው ደስታን ያመጣል ራስን ለማየት ከራስ ጋር ለመምከር የቆሸሸ ህሊናን
ፈውስን ለማጽዳት የሚፋጅ የሚያቃጥል ነገር ሲያጋጥም ነቅነቅ ወዝወዝ
እያደረጉ ለማብረድ ለማቀዝቀዝ ጥሩ ነው
ይህ ሐይል ያለው
ሸፈሮ የተወጠረውን ስሜት ሲያላላው፥ የታመቀ
የጋልታምቤን ትንፋሹን እያንቦለቦለ አስወጥቶ እሁ! አለ ዳሚ አየችው የደሙ
ዝውውር ተረጋግቶ ይሽከረከራል: ገፅታው ጠይቂኝ ይላል"
"ዛሬ ቀን ምን ሆነሃል?" ስትለው ትክ ብሎ አያትና ዐይኖቹን ከላይዋ ላይ አንስቶ ከራሱ ጋር ሙግት ገጠመ" ይህች ሰው
ባትሰማው ይሻል ይሆን? ይህማ የማይቀር እዳዋ ነው ከሌላ ከምትሰማው እኔ ብነግራት አይሻልም አአይ ይቅርባት ትጨነቃለች ችግሩ ደግሞ ወደሷ እየገሰገሰ ነው መከራዋን በቀስ እየደራረበች ብትሸከመው አይሻልም … ብሎ ፊቱን ወደ ዳሚ
መለሰው
"ዳሚ!"
"ዬ!" አለችው ዐይኖችዋን ከዐይኑ ነቅላ እሳት እሳቱን እያየች አይን አፋርነቷ
ትልቁ ውበቷ ነው" ሁሌም ሲጠራት ዐይኗ
ይንከራተትና የሆነ ቦታ ገብቶ ውሽቅ ይላል" የምታየው ግን እሱን ነው።
"ዳሚ!" አላት ደግሞ
"ዬ!" አለችው ድምጿን ከረር አድርጋ እየሰማሁህ ነው'
ለማለት።
"ያች ልጅ መንጠፏ ነው ይሆን?" አላት የሃሣብ ሸክሙን በጥሶ ላይዋ ላይ በትኖ ዳሚ ጥያቄውን ስትሰማ ህሊናዋ አስደንጋጭ ነጎድጓድ ባረቀበት ክው ብላ ደነገጠች አልጮኸችም መልስም አልሰጠችም ውስጧ ግን ባንዴ ባዶ ሆነ ቀፎ ዐይኖችዋን እሳቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ተክላ ቆየች
ጥያቄው በቀፎው ሰውነቷ
እየተንጎዳጎደ ነዘራት አመማት እንደ ሚጥሚጣ ለበለባት ... እሳቱ
ላይ የተሰካው ዐይኗ ሙቀቱ እንዳቀለጠው ሁሉ በፈሳሽ ተሞላ በእንባ በምሬት የዐይኗ ኳስ ሲንቀሳቀስ ግን እንባዋ ፈሰሰ እንባዋን ንፍጧ ጠርቶት ቁልቁል ወረደ እንባዋ ንፍጧን ተከተለው አያት ጋልታምቤ እንደገና በዐይነ-ህሊናው ራሱን አየው፤ እንደ
ከስኬ ወንዝ ወደ ውስጡ የሚሰርገው እንባው ስለማይፈስ መውጫ
ስለሌለው የሰራ አካላቱ ላይ የእንባ ጎርፍ ተኝቶበታል"
"ሁለት ዓመት ሙሉ ይኸው ወልዳ ለመሳም አልታደለችም የሐመር ሽማግሎችም ተነጠፈች በሐመር ደንብ መሰረት ለከሎ ወይ ምትክ ይሰጠው ካለበለዚያም ጥሎሹ ይመለስ እያሉ ነው" አላትና
መሬቷን ተመለከታት ዳሚ የሚለውን አልሰማችውም ከፊት ለፊቱ ተቀምጣ እሷ ግን የለችም አትንቀሳቀስም:
ጋልታምቤ ከውስጥ የዳሚ ከውጭ የላሞች ሳግ ተሰማው የጥጆች ጥሪ የጎይቲ ሰቆቃ
መሀን ሴት በሐመር ልቧ እንደ አሮጌ ቅል የተጠረማመሰ ምስጥ እንዳነካከተው ግንድ ተስፋዋ ፍርክስክስ ያለ ከዚህ መከራዋ በተጨማሪም ቤተሰቧን የመጥፎ ቤተሰብ የምታሰኝ እሷ የመጣችበትን መንገድ ለሌላው ግን የምትከለክል
እርጉም ተብላ
ከማህበራዊው ቡድን ተነጥላ ተወርውራ የምትጣል የቤተሰቧን ጎጆ
በጨለማ የምትሸፍን ናት
"የፈራሁት ደረሰ! ብላ ዳሚ የእንባዋን ውታፍ ከፈተችው
ልቧን ነደለችው ሆን ብላ ያዳፈነችውን የጭንቀት እሳት እፍ አለችው የእንባ ፈሳሽ ያገኘው ስሜቷ እንደ ደረቀ ቅጠል በውስጧ
ሲንቀለቀል ናጣት አርገፈገፋት አስቃሰታት
ስለዚህ ጋልታምቤ ጭንቀቷን ተቀምጦ ማየት ሰቀጠጠው
ከተቀመጠበት ተነስቶ ጥጆችን ከእናታቸው ያራክባቸዋል ከጥቂት ደቂቃ በኋላ አንዱ ጠብቶ ሌላው
ሊያራክባቸው ወጣ ጥጆችን
አጥብቶ ጥጋብ ይሆንና የመለያየቱ ምልክት ድራሹ ጠፍቶ መላላስና
መቦረቅ ይመጣል አንተነህ ይመር ለጎይቲ ምኑን አጥብቶ ከጭንቀቷ
ይገላግላታል! አለኝታው፡ መስታዋቱ ደስታውን እንዳያይባት መከራ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
ካለወትሮው እያከታተለ የሚወርደው ዝናብ የሐመርን ምድር:
የወሮን መንደር የብርሃን ጥላ አልብሷታል" ሰማዩ ላይ በጨርቅ እንደተጠቀለለ ህፃን ዳመናው እየተገለባበጠ
ምርር ብሎ እየጮኸ
ብልጭታው በሁሉም አቅጣጫ ይፈነጣጠቃል
ከክቧ የሐመሮች ጎጆ የሚትጎለጎለው
ከሚጥመለመለው ጥቁር ዳመና ጋር እየተደባለቀ ይጠፋል ፍየሎች በጎች ጥጆች ገና ከበረታቸው አልወጡም በከብቶች አንገት የተንጠለጠለው የኤሊ ድንጋይ ከብቶቹ በተንቀሳቀሱ ቁጥር
ቋቋ ቋቋ እያለ ይሰማል" መንደሯ ልብ ብለው ሲያዳምጧት ትንፋሽዋ እንደወትሮዋ ነው፤ ማነጠሱ፥ ጨዋታው፥ እንጉርጉሮው: ቀልዱ ወፍጮው፥ የወፎቹ ዝማሬ ሁሉም ከዘመናት በፊት
እንደተቃኘው ነው
የናት ጉያ ሙቀት የናፈቃቸው ሆዳቸውን የሞረሞራቸው ጥጆች ግን ከናታችን አራክቡን በሚል ሆድን በሚያላውስ ቅላፄ እ-
ም--ዋ … እም-ቡ-ዋ እያሉ የጌቶቻቸውን ጆሮና ቀልብ ለመሳብ ረሃብና ናፍቆታቸውን በለሆስታ ዜማ አለዝበው ያንጎራጉራሉ" ላሞች እንደሌሎች ከብቶች ማመንዠካቸውን አቁመው ፊታቸውን ወደ ጥጆቻቸው አዙረው ዐይናቸውን እያቁለጨለጩ: ሳጋቸውን እያሰሙ የጥጆችን ከለላ በአፍንጫቸው እያሸተቱና
እየነካኩ የናትነት አንጀታቸው ረፍት ነስቶ ያንሰፈስፋቸዋል አንተነህ ይመር ከምድጃው ጎን ካለችው ትንሽ መደብ ላይ
በቦርኮታው የቀኝ ጭኑን አስደግፎ፥ ጎኑን እሳቱን እያሞቀ እሱም
የማይሰማ ውስጡ ፈልቶ እዚያው ተኖ የሚቀረውን ሳጉን ራሱ ለራሱ ይሰማል
ባለቤቱ እሳቱን እየቆሰቆሰች ሻላው (ቆጡ) ላይ ባሰረችው ጠፍር የአንጠለጠለችውን እርጎ በቀኝ እጅዋ ወደ ፊትና ኋላ
ትንጣለች ቅቤ ለማውጣት ነጭና ጥቁር መልክ ያለው ቁርበት ከበስተ ኋላዋ ተነጥፏል ዳሚ ሰረቅ እያደረገች ስታየው ቆይታ
"ይእ! ምን ሆነሃል የኔ ጌታ?" አለችው
ቢጨንቃት" እሱ ግን ዝም አላት ዝም እየተነፈሰ ጭጭ
"ተቡኑ ልስጥህ?"
ጋልታምቤ መልስ ሳይሰጣት ውጭውን
አየው በጠባቧ በር በግድግዳው ቀዳዳ አየሩ ክርስስ ያለ ነው ቀዝቃዛ የሱም ልብ ቀዝቅዛለች
በሐመር ባህል የተጠየቀ ሁሉ ወዲያው የመመለስ ግዴታ የለበትም አዋቂ አስተሳሰቡ የበሰለ ከመናገሩ በፊት ልቡን ዐይኑ ላይ ማውጣት አለበት በልቦናው የሚያይ ሐሳቡ ሚዛናዊ ሆነ ክፉና ደግ ለመለየት በቃ ሃላፊነት ለመቀበል ደረሰ ማለት ነው" ጋልታምቤም በዚህ መላ
የሚስቱን ጥያቄና ጭጋጋማውን ቀን በልቦናው አየው" ልቦናው ግን ምንም እንዲል አልፈቀደለትም
ዝምታ ደግሞ በራሱ ቋንቋ ነው ዝምታና ዐይን ዝምታና ጥርስ ዝምታና ዝም በአይነቱ የተለያዬ ትርጉም አላቸው በቢጫው በሬ ምድር በሐመር።
ዳሚ የጋልታምቤን ዝምታና ዐይን አይታ የሚያሳስበው ነገር እንዳለ አውጥቶ ሊነግራት ግን እንዳልፈለገ ተረዳች ያን ጊዜ።
ይእ! ምን ሆነ? እንግዲ ተሱ ይምጣ'ንጂ እኔ ምናባቴ
ላርግለት ብላ እሷም ዝም አለች ዝም ተባባሉ እሱና እሷ እሱና እሱ: እሱና ተፈጥሮ ተዘጋጉ"
ጋልታምቤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሰረቅ አድርጎ አያት ልቧን ከንፈሯ ላይ ተቀምጦ አየው ፍርሃት ነፋ ልትት፤ ነፋ ልትት
ሲያደርገው ሲገፋፋው ሲያንቀጠቅጠው ሲያወዛውዘው ተመለከተው
ዳሚ ከበስተግራዋ ተሰካክተው ከተቀመጡት በጨሌ ያጌጠውን
ሾርቃ አንስታ ጠረግ ጠረግ በማድረግ ከተወዘተው እንስራ በቅል ጭልፋ ሸፈሮ ቡና ቀድታ አቀበለችው
ጋልታምቤ እግሩን አንፈራጦ ተቀበላትና ግራ ቀኝ ፊትና ኋላ ጎለል ጎለል አድርጎ አበረደው ከዚያ እፉት ብሎ ፕስስ አድርጎ አማተበ ሸፈሮ ቡና የቦርጆ ፍሬ ሽፋን ነው ደስታን ያመጣል ራስን ለማየት ከራስ ጋር ለመምከር የቆሸሸ ህሊናን
ፈውስን ለማጽዳት የሚፋጅ የሚያቃጥል ነገር ሲያጋጥም ነቅነቅ ወዝወዝ
እያደረጉ ለማብረድ ለማቀዝቀዝ ጥሩ ነው
ይህ ሐይል ያለው
ሸፈሮ የተወጠረውን ስሜት ሲያላላው፥ የታመቀ
የጋልታምቤን ትንፋሹን እያንቦለቦለ አስወጥቶ እሁ! አለ ዳሚ አየችው የደሙ
ዝውውር ተረጋግቶ ይሽከረከራል: ገፅታው ጠይቂኝ ይላል"
"ዛሬ ቀን ምን ሆነሃል?" ስትለው ትክ ብሎ አያትና ዐይኖቹን ከላይዋ ላይ አንስቶ ከራሱ ጋር ሙግት ገጠመ" ይህች ሰው
ባትሰማው ይሻል ይሆን? ይህማ የማይቀር እዳዋ ነው ከሌላ ከምትሰማው እኔ ብነግራት አይሻልም አአይ ይቅርባት ትጨነቃለች ችግሩ ደግሞ ወደሷ እየገሰገሰ ነው መከራዋን በቀስ እየደራረበች ብትሸከመው አይሻልም … ብሎ ፊቱን ወደ ዳሚ
መለሰው
"ዳሚ!"
"ዬ!" አለችው ዐይኖችዋን ከዐይኑ ነቅላ እሳት እሳቱን እያየች አይን አፋርነቷ
ትልቁ ውበቷ ነው" ሁሌም ሲጠራት ዐይኗ
ይንከራተትና የሆነ ቦታ ገብቶ ውሽቅ ይላል" የምታየው ግን እሱን ነው።
"ዳሚ!" አላት ደግሞ
"ዬ!" አለችው ድምጿን ከረር አድርጋ እየሰማሁህ ነው'
ለማለት።
"ያች ልጅ መንጠፏ ነው ይሆን?" አላት የሃሣብ ሸክሙን በጥሶ ላይዋ ላይ በትኖ ዳሚ ጥያቄውን ስትሰማ ህሊናዋ አስደንጋጭ ነጎድጓድ ባረቀበት ክው ብላ ደነገጠች አልጮኸችም መልስም አልሰጠችም ውስጧ ግን ባንዴ ባዶ ሆነ ቀፎ ዐይኖችዋን እሳቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ተክላ ቆየች
ጥያቄው በቀፎው ሰውነቷ
እየተንጎዳጎደ ነዘራት አመማት እንደ ሚጥሚጣ ለበለባት ... እሳቱ
ላይ የተሰካው ዐይኗ ሙቀቱ እንዳቀለጠው ሁሉ በፈሳሽ ተሞላ በእንባ በምሬት የዐይኗ ኳስ ሲንቀሳቀስ ግን እንባዋ ፈሰሰ እንባዋን ንፍጧ ጠርቶት ቁልቁል ወረደ እንባዋ ንፍጧን ተከተለው አያት ጋልታምቤ እንደገና በዐይነ-ህሊናው ራሱን አየው፤ እንደ
ከስኬ ወንዝ ወደ ውስጡ የሚሰርገው እንባው ስለማይፈስ መውጫ
ስለሌለው የሰራ አካላቱ ላይ የእንባ ጎርፍ ተኝቶበታል"
"ሁለት ዓመት ሙሉ ይኸው ወልዳ ለመሳም አልታደለችም የሐመር ሽማግሎችም ተነጠፈች በሐመር ደንብ መሰረት ለከሎ ወይ ምትክ ይሰጠው ካለበለዚያም ጥሎሹ ይመለስ እያሉ ነው" አላትና
መሬቷን ተመለከታት ዳሚ የሚለውን አልሰማችውም ከፊት ለፊቱ ተቀምጣ እሷ ግን የለችም አትንቀሳቀስም:
ጋልታምቤ ከውስጥ የዳሚ ከውጭ የላሞች ሳግ ተሰማው የጥጆች ጥሪ የጎይቲ ሰቆቃ
መሀን ሴት በሐመር ልቧ እንደ አሮጌ ቅል የተጠረማመሰ ምስጥ እንዳነካከተው ግንድ ተስፋዋ ፍርክስክስ ያለ ከዚህ መከራዋ በተጨማሪም ቤተሰቧን የመጥፎ ቤተሰብ የምታሰኝ እሷ የመጣችበትን መንገድ ለሌላው ግን የምትከለክል
እርጉም ተብላ
ከማህበራዊው ቡድን ተነጥላ ተወርውራ የምትጣል የቤተሰቧን ጎጆ
በጨለማ የምትሸፍን ናት
"የፈራሁት ደረሰ! ብላ ዳሚ የእንባዋን ውታፍ ከፈተችው
ልቧን ነደለችው ሆን ብላ ያዳፈነችውን የጭንቀት እሳት እፍ አለችው የእንባ ፈሳሽ ያገኘው ስሜቷ እንደ ደረቀ ቅጠል በውስጧ
ሲንቀለቀል ናጣት አርገፈገፋት አስቃሰታት
ስለዚህ ጋልታምቤ ጭንቀቷን ተቀምጦ ማየት ሰቀጠጠው
ከተቀመጠበት ተነስቶ ጥጆችን ከእናታቸው ያራክባቸዋል ከጥቂት ደቂቃ በኋላ አንዱ ጠብቶ ሌላው
ሊያራክባቸው ወጣ ጥጆችን
አጥብቶ ጥጋብ ይሆንና የመለያየቱ ምልክት ድራሹ ጠፍቶ መላላስና
መቦረቅ ይመጣል አንተነህ ይመር ለጎይቲ ምኑን አጥብቶ ከጭንቀቷ
ይገላግላታል! አለኝታው፡ መስታዋቱ ደስታውን እንዳያይባት መከራ
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እናቷ ሌላ ነገር ለመናገር ከንፈራቸውን ለማነቃነቅ ሲሞክሩ በራፉ ተቆረቆረ …እጃቸው ላይ ባለው ናፕኪን እንባቸውን እያበሱ ሄደው ሲከፍቱ ዶክተሩና መድህኔ ተከታትለው ወደውስጥ ገቡ…፡፡
‹‹ደግሞ ለእሱ ማን ደወለ…?››ልዩ ነች በውስጧ ያልጎመጎመችው፡፡ ወዲያው መልሱን አገኘችው..መድህኔ እነሱ ቤት ውስጥ ከዘበኛ አንድ ከቤት ሰራተኛ አንድ የእሷን የቤት ውስጥ እቅስቃሴ የሚሰልሉ ጆሮ ጠቢዎች እንዳሉት በእርግጠኝነት ታውቃለች…..በዚህም አልተሳሳተችም አሁን ደውለው የነገሩት እነሱ ናቸው..መድህኔ የልጅነት ጓደኛዋ ብቻ ሳይሆን እጮኛዋ ነው…፡፡
‹‹ልዩ..ምን ተፈጥሮ ነው..?እንዴት ሳትደውይልኝ….?ማሚስ ብትደውይልኝ..ምን አለበት…?››
‹‹ያው ተደውሎልህ መጣህ አይደል?›› መሽቆጥቆጡ አበሳጭቷት የመለሰችለት ልዩ ነች፡፡
‹‹አረ እኔ ስልክሽ ከጥዋት ጀምሮ አልሰራ ስላለኝ ግራ ገብቶኝ ለማጣራት ስመጣ ነው በራፍ ላይ ያለው ዘበኛ የነገረኝ››አላት….
ቀኑን ሙሉ ስለእሷ ሲያስብና ሲጨነቅ መዋሉን አልዋሻትም…ግን አሁን እዚህ ሊገኝ የቻለበት ምክንያት እሱ እንዳለው ሳይሆን ልዩ እንደገመተችው ዘበኛው ደውሎ የልዩን መጎዳት ነግሮት ነው በድንጋጤ እያለከለከ ካለበት በሮ የመጣው፡፡
ዶክተሩ ይዟቸው በመጣቸው ዕቃዎች አገላብጦ መረመራትና ቀድሞ የተደረገላት ህክምና እና የተሰጣትን ኪኒን ካየ በኃላ‹‹ወ/ሮ ጥሩነሽ ተገቢው ህክምና ስለተሠጣት ለጊዜው ሌላ ተጨማሪ ነገር አያስፈልግም… ምግብ ትውሰድ ፤እረፍት ታግኝ….ነገ ተመልሼ መጥቼ አያታለሁ››ብሎ እቃውን ሰብስቦ ወጥቶ ሄደ፡፡ ሶስቱ ብቻ ቀሩ፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው ፍቅር ?››ቅልስልስ ባለ ንግግር ጠየቃት፡
እሷ ልትመልስለት አፏን ከመክፈቷ በፊት እናቷ ጣልቃ ገብተው ይመልሱላት ጀመር…‹‹ጓደኞቾ ሲጣሉ ለማገላገል መሀከል ገብታ እንደዚህ ሆነች..እስኪ ቢጫረሱ ምን አገባሽ…?››
እናቷ ገመና ከታች መሆቸው ነው….እጮኛዋ በድርጊቷ እንዳይከፋው ለመከለላከል ነው እንደዛ ያደረጉት…ልጃቸው ስለተፀናወታት መጥፎ ልክፍት ከእሱ በላይ ደግሞ የእሱ ቤተሰቦች እንዳይሰሙ አብዝተው ይጨነቃሉም፤ ይሳቀቃሉም..
የመድሀኔ ቤተሰቦች ከእሳቸው በላይ ወግ አጥባቂና ለክብራቸው አብዝተው ሚጨነቁ ናቸው..አባትዬው እኔ የቀኝ አዝማች ገ/እግዚያብሄር ሀጎስ ልጅ…›› የዘወትር ፉከራቸው ነው…የልዩ እናት አባታቸው ፊት አውራሪ ቢሆንም በግልፅ ሲፎክሩበት ሰምታ አታውቅም….ግን ነገረ ስራቸውና ተግባራቸው ያው በአጥንት ቆጠራ ታሪክ ውስጥ እናቷም እንዳሉበት ታውቃለች፡፡ …አንዳንዴ ሰዎች ሲያበሳጯቸው‹‹ እኔ ከማንም ወፍ ዘራሽ ጋር ዝቅ ብዬ አፍ አልካፈትም›ሲሉ ብዙ ጊዜ ሰምታለች…‹‹አረ ተው የአባቴ መንፈስ ይታዘበኛል›› የሚሉትም ነገር አላቸው.. .እንግደህ ልዩና መድህኔ የሁለት ፊውዳል ቤተሰቦች ውጤት ናቸው…ጥምረታቸውም ፍቅርን ብቻ መሰረት ያደረገ ሳይሆን የቤተሰብም የእጅ አዙር ፍላጎት ያለበት ነው….፡፡›
መድህኔ ወቀሳውን ቀጠለ‹‹ፍቅር እንዴት እንዲህ ታርጊያለሽ.. ? ቀጥታ አይንሽን አግኝተውት ቢሆንስ? ››
‹‹አሁን የእውነት የሆነ የማላውቀው ወንድ መኝታ ቤቱ ድረስ ሰተት ብዬ ገብቼ አልጋው ላይ ስተኛ ውዬ እንደመጣሁ ቢያውቅ እንዲህ በመንሰፍሰፉ ይቀጥልበት ይሆን…?››ስትል በውስጧ አብሰለሰለች…‹‹አሁን አውቆ ነው አይደል እንዲህ የሚሆነው? እኔን በፀፀት ለመለብለብ… በአንድ ቀን ውስጥ በልቤ ገብቶ እየተገለባበጠ ያለው ልጅ ላይ የሰራሁት ግፍ መች አነሰኝ…››በማለት በውስጧ አሰበችና ተበሳጨች፡፡
አናም በንዴት ውስጥ ሆና መልስ ትሰጠው ጀመረች‹‹ቢሆንም ይጠፋላ.. ሌላ ምን ይሆናል…?›› መለስችለት፡፡
‹‹የአይን መጥፋት ቀላል አደረግሽው?››
‹‹ምን ችግር አለው..አንተም እማዬም ብር አላችሁ… ይገዛል… ይቀየራል..አሁን ደክሞኛል ልተኛ ነው፡፡›› አለችውና ተሸፋፍነች፡፡
‹‹ና ልጄ ደሙ ጭንቅላቷ ላይ ወጥቷል መሰለኝ ብስጭትጭት ትላለች..አረፍ ብላ ስትረጋጋ እናነጋግራታለን፡፡››
‹‹አረ ካልሆነ ዊክ ኢንድ ላይ ኢስትአንቡል ወይም ዱባይ ወስዳትና ትንሽ ሪላክስ አድርጋ ትመጣለች…እኔ በህይወት እያለሁም እሷ እንዲህ ድብርት ውስጥ አትገባም፡፡››
‹‹እስቲ ትረጋጋና …እንማከራለን›››ብለው ይዘውት ወጡ…እሷም ወደጥልቅ ሀሳብ ወስጥ ገባች፡፡
//
በማስመሠል ብቃቷ እልል የተባለለትን አርቲስት ታሰንቃለች።በጓደኞቾ መካከል ስትሆን ፈገግታዋ ከጨረቃ የሚፈነጠቅ ብርሀን በሉት ፤ቤተሠቦቼ ሲያገኙት ጥርሷ እንደጥርስ ኪኒሊክ አስተዎዎቂ ያለገደብ ይፈለቀቃል። አለባበሷ የታሰበበትና ሽክ ያለ ነው።ከእሷ ላይ አንድ እንከን ማውጣት ፀጉር መሠንጠቅ ነው ሚሆነው...ታዲያ የትኛው ስል እይታ ያለው ሰው ነው ወደ ውስጧ ዘልቆ የተሰባበረው እሷነቷን በመገንዘብ ሊያዝንላት የሚችለው...?የትኛውስ ጠንቋይ ነው የነፍሷን መሠንጠቅ በራዕይው አይቶ ፈውስ የሚሆን ቅድስ ዘይት የሚሰጣት?።የትኛውስ የልብ ጓደኛ ነው ውስጧ የተንጣለለውን የሀዘን ባህር አይቶ እንዴ ይህቺ ሴትና ደስታ አይተዋወቁም ብሎ በድፍረት መናገር የሚችለው?።ልቧ ላይ ያረፈውንስ አለምን የሚያህል ጥቁር ጠባሳ የትኛው ምጡቅ ሀኪም ነው አክሞ ሊያድነው የሚችለው?
ከታክሲው ገጠመኝ በኃላ ይሄው ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ቢሆንም ደፍራ ከቤቷ አልወጣችም...አይደለም ከቤቷ ከክፍሏም አልወጣችም…ዶክተሩ ዛሬ ጥዋት መጥቶ የተለባበዱት ፕላስተሮችን አላቆላት ፤ባንዴጁን ከላዮ ላይ ጥሎ ንፁህ ሰው መሆኗን አረጋግጦል ‹‹ለሚያቁነጠንጣሽ ደብርት የሚሆን መድሀኒት››ብሎ የሆኑ ኪኒኖች ሰጥቷት ሄዷል፡፡
አዎ ዶክተሩ እንዳለው ፊቷ ላይ የነበረው እብጠትና ቁስለት ጠፍቷል.. ያንንን መታጠቢያ ክፍል ባለ ትልቅ መስታወት ፊት ለሳዕታት ቆማ በመመልከት አረጋግጣለች..፡፡ነገር ግን ልቧ ላይ ያለው ቋጥኝ የሚያህል እብጠት አሁንም ባለበት እንደተነረተ ነው….ልቧ ላይ የተሞነጫጨረው ቁስለትም እንዳለ ነው...እንደውም መግል ይዟል …፡፡ ሲያመረቅዝ የሚለቀው መጥፎ ጠረን በአፍንጫ እየመጣ እየረበሻት ነው…፡፡ክፋቱ ደግሞ እናቷን ጨምሮ ሁሉም ሰው ለሶስት ቀን ሙሉ ሲረባረብ የነበሩት ፊት ለፊቷ ማንም የሚያየውን አካሏ ላይ የሚገኘውን ጭረት ለማዳን ነው…ስለውስጥ ድማቷ ግን ማንም ቁብ የሰጠው የለም… ዶክተሯንም ጨመሮ…አረ ፍቅረኛዋም ጭምር፡፡
‹‹አሁን ምን ይሰማሻል..?እብጠቱ አካካቢ ያምሻል…?ፊትሽ ላይስ? ›› እነዚህንና መስል ጥያቄዎችን ነው በመጠየቅ የሚያደነዝዟት፡፡
‹‹አሁን ስለ እዛ ልጅ ምን ላድርግ? ››ስትል አሰበች፡፡ከእቤቱ ይዛው የመጣችው ላፐቶፕ ኮመዲኖዋ ላይ ቁጭ ብሎ እያፈጠጠባት ነው… .. እዛ ሀሳብ ውስጥ ከገባች እራስ ምታቷ መቀስቀሱ የታወቀ ስለሆነ ችላ አለችውና የራሷን ላፕቶፕ ወደሚገኝበት አልጋዋ ላይ ወጥታ ከፈተችው..ዩቲዩብ ትንሽ አየችና ወደ ፌስ ቡክ ቀየረችው….ቻት ውስጥ ገባችና ከክላስ ጎደኞቾ ጋር እያወራች ሰላ ድንገት ትናንት ተልኮላት የነበረ የማታውቀን ሚሴጅ አገኘች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እናቷ ሌላ ነገር ለመናገር ከንፈራቸውን ለማነቃነቅ ሲሞክሩ በራፉ ተቆረቆረ …እጃቸው ላይ ባለው ናፕኪን እንባቸውን እያበሱ ሄደው ሲከፍቱ ዶክተሩና መድህኔ ተከታትለው ወደውስጥ ገቡ…፡፡
‹‹ደግሞ ለእሱ ማን ደወለ…?››ልዩ ነች በውስጧ ያልጎመጎመችው፡፡ ወዲያው መልሱን አገኘችው..መድህኔ እነሱ ቤት ውስጥ ከዘበኛ አንድ ከቤት ሰራተኛ አንድ የእሷን የቤት ውስጥ እቅስቃሴ የሚሰልሉ ጆሮ ጠቢዎች እንዳሉት በእርግጠኝነት ታውቃለች…..በዚህም አልተሳሳተችም አሁን ደውለው የነገሩት እነሱ ናቸው..መድህኔ የልጅነት ጓደኛዋ ብቻ ሳይሆን እጮኛዋ ነው…፡፡
‹‹ልዩ..ምን ተፈጥሮ ነው..?እንዴት ሳትደውይልኝ….?ማሚስ ብትደውይልኝ..ምን አለበት…?››
‹‹ያው ተደውሎልህ መጣህ አይደል?›› መሽቆጥቆጡ አበሳጭቷት የመለሰችለት ልዩ ነች፡፡
‹‹አረ እኔ ስልክሽ ከጥዋት ጀምሮ አልሰራ ስላለኝ ግራ ገብቶኝ ለማጣራት ስመጣ ነው በራፍ ላይ ያለው ዘበኛ የነገረኝ››አላት….
ቀኑን ሙሉ ስለእሷ ሲያስብና ሲጨነቅ መዋሉን አልዋሻትም…ግን አሁን እዚህ ሊገኝ የቻለበት ምክንያት እሱ እንዳለው ሳይሆን ልዩ እንደገመተችው ዘበኛው ደውሎ የልዩን መጎዳት ነግሮት ነው በድንጋጤ እያለከለከ ካለበት በሮ የመጣው፡፡
ዶክተሩ ይዟቸው በመጣቸው ዕቃዎች አገላብጦ መረመራትና ቀድሞ የተደረገላት ህክምና እና የተሰጣትን ኪኒን ካየ በኃላ‹‹ወ/ሮ ጥሩነሽ ተገቢው ህክምና ስለተሠጣት ለጊዜው ሌላ ተጨማሪ ነገር አያስፈልግም… ምግብ ትውሰድ ፤እረፍት ታግኝ….ነገ ተመልሼ መጥቼ አያታለሁ››ብሎ እቃውን ሰብስቦ ወጥቶ ሄደ፡፡ ሶስቱ ብቻ ቀሩ፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው ፍቅር ?››ቅልስልስ ባለ ንግግር ጠየቃት፡
እሷ ልትመልስለት አፏን ከመክፈቷ በፊት እናቷ ጣልቃ ገብተው ይመልሱላት ጀመር…‹‹ጓደኞቾ ሲጣሉ ለማገላገል መሀከል ገብታ እንደዚህ ሆነች..እስኪ ቢጫረሱ ምን አገባሽ…?››
እናቷ ገመና ከታች መሆቸው ነው….እጮኛዋ በድርጊቷ እንዳይከፋው ለመከለላከል ነው እንደዛ ያደረጉት…ልጃቸው ስለተፀናወታት መጥፎ ልክፍት ከእሱ በላይ ደግሞ የእሱ ቤተሰቦች እንዳይሰሙ አብዝተው ይጨነቃሉም፤ ይሳቀቃሉም..
የመድሀኔ ቤተሰቦች ከእሳቸው በላይ ወግ አጥባቂና ለክብራቸው አብዝተው ሚጨነቁ ናቸው..አባትዬው እኔ የቀኝ አዝማች ገ/እግዚያብሄር ሀጎስ ልጅ…›› የዘወትር ፉከራቸው ነው…የልዩ እናት አባታቸው ፊት አውራሪ ቢሆንም በግልፅ ሲፎክሩበት ሰምታ አታውቅም….ግን ነገረ ስራቸውና ተግባራቸው ያው በአጥንት ቆጠራ ታሪክ ውስጥ እናቷም እንዳሉበት ታውቃለች፡፡ …አንዳንዴ ሰዎች ሲያበሳጯቸው‹‹ እኔ ከማንም ወፍ ዘራሽ ጋር ዝቅ ብዬ አፍ አልካፈትም›ሲሉ ብዙ ጊዜ ሰምታለች…‹‹አረ ተው የአባቴ መንፈስ ይታዘበኛል›› የሚሉትም ነገር አላቸው.. .እንግደህ ልዩና መድህኔ የሁለት ፊውዳል ቤተሰቦች ውጤት ናቸው…ጥምረታቸውም ፍቅርን ብቻ መሰረት ያደረገ ሳይሆን የቤተሰብም የእጅ አዙር ፍላጎት ያለበት ነው….፡፡›
መድህኔ ወቀሳውን ቀጠለ‹‹ፍቅር እንዴት እንዲህ ታርጊያለሽ.. ? ቀጥታ አይንሽን አግኝተውት ቢሆንስ? ››
‹‹አሁን የእውነት የሆነ የማላውቀው ወንድ መኝታ ቤቱ ድረስ ሰተት ብዬ ገብቼ አልጋው ላይ ስተኛ ውዬ እንደመጣሁ ቢያውቅ እንዲህ በመንሰፍሰፉ ይቀጥልበት ይሆን…?››ስትል በውስጧ አብሰለሰለች…‹‹አሁን አውቆ ነው አይደል እንዲህ የሚሆነው? እኔን በፀፀት ለመለብለብ… በአንድ ቀን ውስጥ በልቤ ገብቶ እየተገለባበጠ ያለው ልጅ ላይ የሰራሁት ግፍ መች አነሰኝ…››በማለት በውስጧ አሰበችና ተበሳጨች፡፡
አናም በንዴት ውስጥ ሆና መልስ ትሰጠው ጀመረች‹‹ቢሆንም ይጠፋላ.. ሌላ ምን ይሆናል…?›› መለስችለት፡፡
‹‹የአይን መጥፋት ቀላል አደረግሽው?››
‹‹ምን ችግር አለው..አንተም እማዬም ብር አላችሁ… ይገዛል… ይቀየራል..አሁን ደክሞኛል ልተኛ ነው፡፡›› አለችውና ተሸፋፍነች፡፡
‹‹ና ልጄ ደሙ ጭንቅላቷ ላይ ወጥቷል መሰለኝ ብስጭትጭት ትላለች..አረፍ ብላ ስትረጋጋ እናነጋግራታለን፡፡››
‹‹አረ ካልሆነ ዊክ ኢንድ ላይ ኢስትአንቡል ወይም ዱባይ ወስዳትና ትንሽ ሪላክስ አድርጋ ትመጣለች…እኔ በህይወት እያለሁም እሷ እንዲህ ድብርት ውስጥ አትገባም፡፡››
‹‹እስቲ ትረጋጋና …እንማከራለን›››ብለው ይዘውት ወጡ…እሷም ወደጥልቅ ሀሳብ ወስጥ ገባች፡፡
//
በማስመሠል ብቃቷ እልል የተባለለትን አርቲስት ታሰንቃለች።በጓደኞቾ መካከል ስትሆን ፈገግታዋ ከጨረቃ የሚፈነጠቅ ብርሀን በሉት ፤ቤተሠቦቼ ሲያገኙት ጥርሷ እንደጥርስ ኪኒሊክ አስተዎዎቂ ያለገደብ ይፈለቀቃል። አለባበሷ የታሰበበትና ሽክ ያለ ነው።ከእሷ ላይ አንድ እንከን ማውጣት ፀጉር መሠንጠቅ ነው ሚሆነው...ታዲያ የትኛው ስል እይታ ያለው ሰው ነው ወደ ውስጧ ዘልቆ የተሰባበረው እሷነቷን በመገንዘብ ሊያዝንላት የሚችለው...?የትኛውስ ጠንቋይ ነው የነፍሷን መሠንጠቅ በራዕይው አይቶ ፈውስ የሚሆን ቅድስ ዘይት የሚሰጣት?።የትኛውስ የልብ ጓደኛ ነው ውስጧ የተንጣለለውን የሀዘን ባህር አይቶ እንዴ ይህቺ ሴትና ደስታ አይተዋወቁም ብሎ በድፍረት መናገር የሚችለው?።ልቧ ላይ ያረፈውንስ አለምን የሚያህል ጥቁር ጠባሳ የትኛው ምጡቅ ሀኪም ነው አክሞ ሊያድነው የሚችለው?
ከታክሲው ገጠመኝ በኃላ ይሄው ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ቢሆንም ደፍራ ከቤቷ አልወጣችም...አይደለም ከቤቷ ከክፍሏም አልወጣችም…ዶክተሩ ዛሬ ጥዋት መጥቶ የተለባበዱት ፕላስተሮችን አላቆላት ፤ባንዴጁን ከላዮ ላይ ጥሎ ንፁህ ሰው መሆኗን አረጋግጦል ‹‹ለሚያቁነጠንጣሽ ደብርት የሚሆን መድሀኒት››ብሎ የሆኑ ኪኒኖች ሰጥቷት ሄዷል፡፡
አዎ ዶክተሩ እንዳለው ፊቷ ላይ የነበረው እብጠትና ቁስለት ጠፍቷል.. ያንንን መታጠቢያ ክፍል ባለ ትልቅ መስታወት ፊት ለሳዕታት ቆማ በመመልከት አረጋግጣለች..፡፡ነገር ግን ልቧ ላይ ያለው ቋጥኝ የሚያህል እብጠት አሁንም ባለበት እንደተነረተ ነው….ልቧ ላይ የተሞነጫጨረው ቁስለትም እንዳለ ነው...እንደውም መግል ይዟል …፡፡ ሲያመረቅዝ የሚለቀው መጥፎ ጠረን በአፍንጫ እየመጣ እየረበሻት ነው…፡፡ክፋቱ ደግሞ እናቷን ጨምሮ ሁሉም ሰው ለሶስት ቀን ሙሉ ሲረባረብ የነበሩት ፊት ለፊቷ ማንም የሚያየውን አካሏ ላይ የሚገኘውን ጭረት ለማዳን ነው…ስለውስጥ ድማቷ ግን ማንም ቁብ የሰጠው የለም… ዶክተሯንም ጨመሮ…አረ ፍቅረኛዋም ጭምር፡፡
‹‹አሁን ምን ይሰማሻል..?እብጠቱ አካካቢ ያምሻል…?ፊትሽ ላይስ? ›› እነዚህንና መስል ጥያቄዎችን ነው በመጠየቅ የሚያደነዝዟት፡፡
‹‹አሁን ስለ እዛ ልጅ ምን ላድርግ? ››ስትል አሰበች፡፡ከእቤቱ ይዛው የመጣችው ላፐቶፕ ኮመዲኖዋ ላይ ቁጭ ብሎ እያፈጠጠባት ነው… .. እዛ ሀሳብ ውስጥ ከገባች እራስ ምታቷ መቀስቀሱ የታወቀ ስለሆነ ችላ አለችውና የራሷን ላፕቶፕ ወደሚገኝበት አልጋዋ ላይ ወጥታ ከፈተችው..ዩቲዩብ ትንሽ አየችና ወደ ፌስ ቡክ ቀየረችው….ቻት ውስጥ ገባችና ከክላስ ጎደኞቾ ጋር እያወራች ሰላ ድንገት ትናንት ተልኮላት የነበረ የማታውቀን ሚሴጅ አገኘች፡፡
#ህያብ
:
:
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
አንዳንዶች ለወደዱት ብቻ ጥሩ ይሆናሉ.... አንዳንዶች ደግሞ እንዲሁ በተፈጥሯቸው ጥሩነትን ይታደሉታል። ቢኒ እንደዛ ነው መልካምነትን የታደለ ጥሩ ልብ ያለው ልጅ ነው። ድሀ ወይም ሀብታም፣ ክርስቲያን ሙስሊም ወይም ሌላ እምነት፣ ቆንጆ ወይም መልከ ጥፉ፣ ቢኒ ጋር መስፈርት አይደሉም። ለሁሉም እኩል ፍቅርና እንክብካቤ ሲሰጥ ታዩታላችሁ..... ግቢ ውስጥም ሆነ ከተማ ውስጥ ያሉ የበጎ አድራጎት ስራዎች አያመልጡትም.....
"ቢኒዬ ግን እርግጠኛ ነህ እዚህ ብሆን አረብሽህም.." እረጅም ሰዓት ተጨቃጭቀን እስከፈለኩ ድረስ ቤቱ እንድኖር ከነገረኝ በኋላ ሀሳቡን ቢቀይር ብዬ ጠየኩት
አጠገቤ መጣና ቁጭ አለ.... እጆቹን ልኮ ሁለት እጆቼን ያዘና አይን አይኔን እያዬ "ህዩ አንቺ ጓደኛዬ ነሽ... ጓደኝነት ውስጥ ደግሞ እኔ የሚባል ነገር የለም በተለይ እኔ ካንቺ እኔን ላስቀድም አልችልም ምክንያቱም......" ከንፈሮቹ ተንቀጠቀጡ።
"ምክንያቱም ምን ቢኒዬ" እጄን ለቆ ተነሳና ጀርባውን ሰቶኝ ከመስኮት ዳር ቆመ።
"ህያብ ጊዜ የነገሮች ጌታ ነው ብዬ አምናለሁ... እናም ሁሉም በጊዜው ሲሆን ደስ ይላል። አሁን ከኔ ምክንያት በላይ ያንቺ ሁኔታዎች ናቸው መስተካከል ያለባቸው...." ክትክት ብዬ ሳቅሁ... የእብደት ሳቅ
ከሳቄ በኋላ
" እስኪ ንገረኝ ምኑን ነው የምታስተካክለው.... እናቴን ልጄን ወይስ ከሀዲው ባሌን ማንን መልሰህ ልታመጣልኝ የምትችል ይመስልሀል..." ድጋሚ አመመኝ... መቋቋም አቃተኝ... በሁለት እጄ ጭንቅላቴን ጥፍንግ አድርጌ ያዝኩት። የሆነ ሽክርክሪት ውስጥ እንዳለሁ ይሰማኛል ዥውውውውውውውው.... ሳቅ ከዛ ደግሞ ዝምምምምታ.... ከዛ ደግሞ ሌላ ሳቅ.... ይሄኛው አለም የተሻለ ይመስለኛል።
የሆነ ሰው አፌ ውስጥ የሆነ ነገር ለማስገባት ታገለኝ አልከለከልኩትም ዋጥኩት ከዛ ሁሉም ነገር ፀጥ አለ።
ምን ሰዓት እንደተኛሁ ባላውቅም ራሴን ጋቢ ለብሼ ሶፋ ላይ ተኝቼ አገኘሁት። ቀና ብዬ ተስተካክዬ ቁጭ ስል ቢኒን ከእግሬ ስር ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቅዱስ ሲያነብ አየሁት።
"ይቅርታ ቢኒ ረበሽኩህ መሰለኝ.." መፅሀፍ ቅዱሱን ዘግቶ ከሳመ በኋላ የኔንም ግንባር ነካ አደረገበትና ተነስቶ አስቀምጦ ተመለሰ።
"ሁለተኛ እንደዚህ እንዳትይኝ ማስቸገር ገለመሌ የሚባል ታሪክ የለም ያራቅሺኝ ነው የሚመስለኝ..."
"እሺ በቃ አይለመደኝም..... ይልቅ እስኪ ንገረኝ የውጪ ቆይታህ እንዴት ነበር የተመለስከውስ መች ነው"
"ቆይታዬን በደፈናው ጥሩ ነበር ልበልሽ መሰለኝ። የተመለስኩት ሁለት ወር አካባቢ ሆነኝ ግን ቀጥታ ቤተሰብ ጋር ክፍለ ሀገር ነው የሄድኩት ከተመለስኩ ገና ሳምንትም አልሞላኝ"
"እና ለምን ልትፈልገኝ ወደ ቤት አልመጣህም..." ክፍት ነው ያለኝ ምንም እንኳን የሱን ስም ሲሰማ ባሌ ቢናደድም ቢኒ ላጣው የማልፈልገው ጓደኛዬ ነው እና እንዴት...
"ወዳንቺ ጋር እየመጣሁ እያለ እኮ ነው መኪና ውስጥ የገባሽብኝ"
"ኦ እሺ እንደዛ ከሆነ"
"አልተዋጠልሽም አይደል ህያቤ ብዙ ጊዜ እንዳልደወልኩልሽ አውቃ..." አቋረጥኩት
"ምን ብዙ ጊዜ ትላለህ ከሄድክ ጀምሮ ሁለቴ ብቻ እኮ ነው የደወልከው.... እናም አልዋሽህም ተቀይሜሀለሁ"
"ምክንያቴን ስታውቂ እንደምትረጂኝ ስለማውቅ ችግር የለውም.... የሆነ ነገር መብላት አለብን ምን ትፈልጊያለሽ..." አለኝ ወደ ኪቺን እየገባ
"ፍላጎትሽን አትናገሪም ካለዛ ዱባ ወጥ ነው የምሰራው ሀ ሀ ሀ" ሽርጡን አገልድሞ ብቅ አለ
" ዱባ ስራና ሶስት ቀን ውጪ አሳድሬ ነው የማበላህ.... አንተ ደግሞ ሼፍ መስለህ የለም እንዴ"
"ነይ አሁን ተነሺ ቢያንስ ዱባውን እንኳን በመክተፍ አግዢኝ" ከስሙ ጭምር እንደምጠላው ስለሚያውቅ እኮ ነው ...ዱባን....
"ሀ ሀ ሀ አንተ እብድ ትቀልድብኛለህ አ" ከረጅም ጊዜ በኋላ ሳቅሁ
......
፨፨፨ ፨፨፨፨ ፨፨፨፨
ጎንደር ዩንቨርስቲ ሁለተኛ አመት
"ቢኒ ዮናታንን እወደዋለሁ ከዚህ በላይ መቋቋም አልችልም እናም እነግረዋለሁ"
"ህያብ ዮናታንን ታውቂዋለሽ.... እሺ አለሽ እንበል ከዛ እነኝህን ሁሉ ሴቶች ትቶ ካንቺ ጋር ብቻ የሚሆን ይመስልሻል"
"አላውቅም ግን እድሌን ልሞክር.."
"ተይ ህያብ ይቅርብሽ"
"አይሆንም ቢኒ እድሌን እሞክራለሁ" ይሄን ሁሉ የምንጨቃጨቀው ዮናታን የሚያመሽበት ጭፈራ ቤት በር ላይ ሆነን ነው። ወደ ውስጥ ገባሁ... አይኔን ዞር ዞር እያደረኩ ፈለኩት ጥግ ሶፋ ላይ ከአንዲት ሴት ጋር የተሰፋ ያክል ተጣብቋል.... በደንብ ቀረብኳቸው... አንገቱ ስር ስማው ቀና ስትል አይን ለአይን ተገጣጠምን... የትናዬት....
ደንዝዤ አንደቆምኩ የሆነ ሰው እጅ ትከሻዬ ላይ አረፈ "የኔ ቆንጆ በዛኛው በኩል ቦታ አግኝቻለሁ.... እንሂድ አይደል" ውጪ ቆይ አላልኩትም ነበር.... ቢሆንም ግን ወሳኝ ሰዓት ላይ ነው የደረሰው።
"አየሽ አይደል በራስሽ ላይ ምን እያመጣሽ እንደሆነ"
ሲጀመር እሱን ብቻውን አገኘዋለሁ ብዬ ማሰቤ ነው የኔ ጥፋት እርር ድብን ብሽቅቅቅቅ ብያለሁ እኮ
"አረጋጊው እንጂ ውዷ ጉበትሽን መትፋት አማረሽ እንዴ"
"ተወኝ ባክህ ልጠጣበ" ከነ ጠርሙሱ አንስቼ ለመጠጣት ስሞክር ከእጄ ቀማኝና
"ነይ በቃ እንሂድ ግቢ ይዘጋል" አለኝ
"የትም አልሄድም ተወኝ"
"ይሄንን ነው መፍራት... ኧረ ህያብ በፈጠረሽ..." ጠርሙሱን ተቀብዬው እየተንገዳገድኩ እነሱ ወዳሉበት ቦታ ሄድኩ....
"ህያብ አንቺ ህያብ" የእናቴ ድምፅ መሰለኝ.... እየጠራችኝ ነው።
"አቤት እማ መጣሁ" ብዬ ከተኛሁበት ለመነሳት ስሞክር ሀይለኛ ራስ ምታት አናቴን ይዞ እየፈለጠኝ ነው። ጭንቅላቴን በሁለት እጄ ጥፍንግ አድርጌ ይዤው ከቆየሁ በኋላ አይኔን በደንብ ከፍቼ ሳይ ያለሁት እናቴ ቤት አይደለም....
ከፊት ለፊቴ ቢኒ ተቀምጦ የማደርገውን ነገር ያያል።
"ኡፍፍፍፍ የት ነው ያለሁት ምን ተፈጥሮ ነው.... ቆይ እማዬ የጠራችኝ አልመሰለኝም.."
"ባክሽ እኔ ነኝ የጠራሁሽ ክፍል ልቀቁ እየተባልን ነው ተነሺ..." ቢኒ እንደዚህ አውርቶኝ አያውቅም....
"ምንድነው ቢኒ ችግር አለ እየተነጫነጭክ እኮ ነው ምነው ማታ አስቀየምኩህ እንዴ.... ማታ....ቆይ ቆይ እንዴት ወደዚህ ልመጣ ቻልኩ? ማነው ያመጣኝ? ማለት ምን ተፈጥሮ ነው?..." የጥያቄ መአት አከታተልኩበት
"በመጀመሪያ ተነሽና ታጠቢ ከዛ ወደ ግቢ እንመለስና ዶርም ገብተሽ እረፍት አድርጊ ከዛ ተገናኝተን ጥያቄዎችሽን እመልስልሻለሁ እስከዛው ትዝ የሚልሽ ነገር ካለ ራስሽ ጥያቄሽን መመለስ ትችያለሽ" እንዴ ምንድነው ጉዱ ቢኒ እንደዚ ከረር ብሎ አይቼው አላውቅም ጭራሽ የማላውቀው ሰው ነው የሆነብኝ። ተጨማሪ ጥያቄ ሳልጠይቅ ጭንቅላቴን ደግፌ እየተጎተትኩ መታጠቢያ ቤት ገባሁ።
ሰውነቴ ስብርብር ያለ ያክል እየተሰማኝ ታጥቤ ጨረስኩ
፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨
"አንተ ቢኒ ግን አልተኛህም እንዴ አይንህ እኮ በርበሬ ነው የሚመስለው" ወደ ግቢ እየሄድን ጠየኩት
:
:
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
አንዳንዶች ለወደዱት ብቻ ጥሩ ይሆናሉ.... አንዳንዶች ደግሞ እንዲሁ በተፈጥሯቸው ጥሩነትን ይታደሉታል። ቢኒ እንደዛ ነው መልካምነትን የታደለ ጥሩ ልብ ያለው ልጅ ነው። ድሀ ወይም ሀብታም፣ ክርስቲያን ሙስሊም ወይም ሌላ እምነት፣ ቆንጆ ወይም መልከ ጥፉ፣ ቢኒ ጋር መስፈርት አይደሉም። ለሁሉም እኩል ፍቅርና እንክብካቤ ሲሰጥ ታዩታላችሁ..... ግቢ ውስጥም ሆነ ከተማ ውስጥ ያሉ የበጎ አድራጎት ስራዎች አያመልጡትም.....
"ቢኒዬ ግን እርግጠኛ ነህ እዚህ ብሆን አረብሽህም.." እረጅም ሰዓት ተጨቃጭቀን እስከፈለኩ ድረስ ቤቱ እንድኖር ከነገረኝ በኋላ ሀሳቡን ቢቀይር ብዬ ጠየኩት
አጠገቤ መጣና ቁጭ አለ.... እጆቹን ልኮ ሁለት እጆቼን ያዘና አይን አይኔን እያዬ "ህዩ አንቺ ጓደኛዬ ነሽ... ጓደኝነት ውስጥ ደግሞ እኔ የሚባል ነገር የለም በተለይ እኔ ካንቺ እኔን ላስቀድም አልችልም ምክንያቱም......" ከንፈሮቹ ተንቀጠቀጡ።
"ምክንያቱም ምን ቢኒዬ" እጄን ለቆ ተነሳና ጀርባውን ሰቶኝ ከመስኮት ዳር ቆመ።
"ህያብ ጊዜ የነገሮች ጌታ ነው ብዬ አምናለሁ... እናም ሁሉም በጊዜው ሲሆን ደስ ይላል። አሁን ከኔ ምክንያት በላይ ያንቺ ሁኔታዎች ናቸው መስተካከል ያለባቸው...." ክትክት ብዬ ሳቅሁ... የእብደት ሳቅ
ከሳቄ በኋላ
" እስኪ ንገረኝ ምኑን ነው የምታስተካክለው.... እናቴን ልጄን ወይስ ከሀዲው ባሌን ማንን መልሰህ ልታመጣልኝ የምትችል ይመስልሀል..." ድጋሚ አመመኝ... መቋቋም አቃተኝ... በሁለት እጄ ጭንቅላቴን ጥፍንግ አድርጌ ያዝኩት። የሆነ ሽክርክሪት ውስጥ እንዳለሁ ይሰማኛል ዥውውውውውውውው.... ሳቅ ከዛ ደግሞ ዝምምምምታ.... ከዛ ደግሞ ሌላ ሳቅ.... ይሄኛው አለም የተሻለ ይመስለኛል።
የሆነ ሰው አፌ ውስጥ የሆነ ነገር ለማስገባት ታገለኝ አልከለከልኩትም ዋጥኩት ከዛ ሁሉም ነገር ፀጥ አለ።
ምን ሰዓት እንደተኛሁ ባላውቅም ራሴን ጋቢ ለብሼ ሶፋ ላይ ተኝቼ አገኘሁት። ቀና ብዬ ተስተካክዬ ቁጭ ስል ቢኒን ከእግሬ ስር ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቅዱስ ሲያነብ አየሁት።
"ይቅርታ ቢኒ ረበሽኩህ መሰለኝ.." መፅሀፍ ቅዱሱን ዘግቶ ከሳመ በኋላ የኔንም ግንባር ነካ አደረገበትና ተነስቶ አስቀምጦ ተመለሰ።
"ሁለተኛ እንደዚህ እንዳትይኝ ማስቸገር ገለመሌ የሚባል ታሪክ የለም ያራቅሺኝ ነው የሚመስለኝ..."
"እሺ በቃ አይለመደኝም..... ይልቅ እስኪ ንገረኝ የውጪ ቆይታህ እንዴት ነበር የተመለስከውስ መች ነው"
"ቆይታዬን በደፈናው ጥሩ ነበር ልበልሽ መሰለኝ። የተመለስኩት ሁለት ወር አካባቢ ሆነኝ ግን ቀጥታ ቤተሰብ ጋር ክፍለ ሀገር ነው የሄድኩት ከተመለስኩ ገና ሳምንትም አልሞላኝ"
"እና ለምን ልትፈልገኝ ወደ ቤት አልመጣህም..." ክፍት ነው ያለኝ ምንም እንኳን የሱን ስም ሲሰማ ባሌ ቢናደድም ቢኒ ላጣው የማልፈልገው ጓደኛዬ ነው እና እንዴት...
"ወዳንቺ ጋር እየመጣሁ እያለ እኮ ነው መኪና ውስጥ የገባሽብኝ"
"ኦ እሺ እንደዛ ከሆነ"
"አልተዋጠልሽም አይደል ህያቤ ብዙ ጊዜ እንዳልደወልኩልሽ አውቃ..." አቋረጥኩት
"ምን ብዙ ጊዜ ትላለህ ከሄድክ ጀምሮ ሁለቴ ብቻ እኮ ነው የደወልከው.... እናም አልዋሽህም ተቀይሜሀለሁ"
"ምክንያቴን ስታውቂ እንደምትረጂኝ ስለማውቅ ችግር የለውም.... የሆነ ነገር መብላት አለብን ምን ትፈልጊያለሽ..." አለኝ ወደ ኪቺን እየገባ
"ፍላጎትሽን አትናገሪም ካለዛ ዱባ ወጥ ነው የምሰራው ሀ ሀ ሀ" ሽርጡን አገልድሞ ብቅ አለ
" ዱባ ስራና ሶስት ቀን ውጪ አሳድሬ ነው የማበላህ.... አንተ ደግሞ ሼፍ መስለህ የለም እንዴ"
"ነይ አሁን ተነሺ ቢያንስ ዱባውን እንኳን በመክተፍ አግዢኝ" ከስሙ ጭምር እንደምጠላው ስለሚያውቅ እኮ ነው ...ዱባን....
"ሀ ሀ ሀ አንተ እብድ ትቀልድብኛለህ አ" ከረጅም ጊዜ በኋላ ሳቅሁ
......
፨፨፨ ፨፨፨፨ ፨፨፨፨
ጎንደር ዩንቨርስቲ ሁለተኛ አመት
"ቢኒ ዮናታንን እወደዋለሁ ከዚህ በላይ መቋቋም አልችልም እናም እነግረዋለሁ"
"ህያብ ዮናታንን ታውቂዋለሽ.... እሺ አለሽ እንበል ከዛ እነኝህን ሁሉ ሴቶች ትቶ ካንቺ ጋር ብቻ የሚሆን ይመስልሻል"
"አላውቅም ግን እድሌን ልሞክር.."
"ተይ ህያብ ይቅርብሽ"
"አይሆንም ቢኒ እድሌን እሞክራለሁ" ይሄን ሁሉ የምንጨቃጨቀው ዮናታን የሚያመሽበት ጭፈራ ቤት በር ላይ ሆነን ነው። ወደ ውስጥ ገባሁ... አይኔን ዞር ዞር እያደረኩ ፈለኩት ጥግ ሶፋ ላይ ከአንዲት ሴት ጋር የተሰፋ ያክል ተጣብቋል.... በደንብ ቀረብኳቸው... አንገቱ ስር ስማው ቀና ስትል አይን ለአይን ተገጣጠምን... የትናዬት....
ደንዝዤ አንደቆምኩ የሆነ ሰው እጅ ትከሻዬ ላይ አረፈ "የኔ ቆንጆ በዛኛው በኩል ቦታ አግኝቻለሁ.... እንሂድ አይደል" ውጪ ቆይ አላልኩትም ነበር.... ቢሆንም ግን ወሳኝ ሰዓት ላይ ነው የደረሰው።
"አየሽ አይደል በራስሽ ላይ ምን እያመጣሽ እንደሆነ"
ሲጀመር እሱን ብቻውን አገኘዋለሁ ብዬ ማሰቤ ነው የኔ ጥፋት እርር ድብን ብሽቅቅቅቅ ብያለሁ እኮ
"አረጋጊው እንጂ ውዷ ጉበትሽን መትፋት አማረሽ እንዴ"
"ተወኝ ባክህ ልጠጣበ" ከነ ጠርሙሱ አንስቼ ለመጠጣት ስሞክር ከእጄ ቀማኝና
"ነይ በቃ እንሂድ ግቢ ይዘጋል" አለኝ
"የትም አልሄድም ተወኝ"
"ይሄንን ነው መፍራት... ኧረ ህያብ በፈጠረሽ..." ጠርሙሱን ተቀብዬው እየተንገዳገድኩ እነሱ ወዳሉበት ቦታ ሄድኩ....
"ህያብ አንቺ ህያብ" የእናቴ ድምፅ መሰለኝ.... እየጠራችኝ ነው።
"አቤት እማ መጣሁ" ብዬ ከተኛሁበት ለመነሳት ስሞክር ሀይለኛ ራስ ምታት አናቴን ይዞ እየፈለጠኝ ነው። ጭንቅላቴን በሁለት እጄ ጥፍንግ አድርጌ ይዤው ከቆየሁ በኋላ አይኔን በደንብ ከፍቼ ሳይ ያለሁት እናቴ ቤት አይደለም....
ከፊት ለፊቴ ቢኒ ተቀምጦ የማደርገውን ነገር ያያል።
"ኡፍፍፍፍ የት ነው ያለሁት ምን ተፈጥሮ ነው.... ቆይ እማዬ የጠራችኝ አልመሰለኝም.."
"ባክሽ እኔ ነኝ የጠራሁሽ ክፍል ልቀቁ እየተባልን ነው ተነሺ..." ቢኒ እንደዚህ አውርቶኝ አያውቅም....
"ምንድነው ቢኒ ችግር አለ እየተነጫነጭክ እኮ ነው ምነው ማታ አስቀየምኩህ እንዴ.... ማታ....ቆይ ቆይ እንዴት ወደዚህ ልመጣ ቻልኩ? ማነው ያመጣኝ? ማለት ምን ተፈጥሮ ነው?..." የጥያቄ መአት አከታተልኩበት
"በመጀመሪያ ተነሽና ታጠቢ ከዛ ወደ ግቢ እንመለስና ዶርም ገብተሽ እረፍት አድርጊ ከዛ ተገናኝተን ጥያቄዎችሽን እመልስልሻለሁ እስከዛው ትዝ የሚልሽ ነገር ካለ ራስሽ ጥያቄሽን መመለስ ትችያለሽ" እንዴ ምንድነው ጉዱ ቢኒ እንደዚ ከረር ብሎ አይቼው አላውቅም ጭራሽ የማላውቀው ሰው ነው የሆነብኝ። ተጨማሪ ጥያቄ ሳልጠይቅ ጭንቅላቴን ደግፌ እየተጎተትኩ መታጠቢያ ቤት ገባሁ።
ሰውነቴ ስብርብር ያለ ያክል እየተሰማኝ ታጥቤ ጨረስኩ
፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨
"አንተ ቢኒ ግን አልተኛህም እንዴ አይንህ እኮ በርበሬ ነው የሚመስለው" ወደ ግቢ እየሄድን ጠየኩት
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
እለቱ እሁድ …ሰማይና ምድሩ ከመላቀቁ በፊት በሚባልበት የለሊቱ የጊዜ ክፍል ላይ ነው፡፡ ኦርቶዶክሶቹ ቤተሰቦቾ ተነስተው አምላካቸውን ለመማፀን ቅ/ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተያይዘው ግቢውን ለቀው እንደወጡ እሷም ተስፈንጥራ መኝታዋን ለቀቀችና እቤቱን በታናናሽ ወንድሞቾ ላይ ከውጭ መለስ አድርጋባቸው ግቢውን ለቃ ቁልቁለቱን በመንደርደር እንቅፍት እያላተማት ወደ ያዶት ሩጫዋን ቀጠለች..ይገርማል ጄሬካን እንዳልያዘች እንኳን ትዝ ያላት የወንዙን የለሊት ሿሿታ ድምጽ ለጆሮዋ ከደረሰ በኃላ ነበር፡፡
‹‹ወይ ጉዴ….ምን መሆኔ ነው …? እሱስ እንዴት ይታዘበኝ…?›ስትል በውስጧ እራሷን ታዘበች፡፡
እንደዛም ቢሆንም ግን እርምጃዋን አልጋታችም ….ቀጥታ ወደ ወንዙ አመራች…፡፡ በእለቱ የተለየ መንቀዥቀዥ፤ የተለየ መቀበጥበጥ.፤የተለየ መቁላላት 🤭 እየታየባት ነበር… ምክንያቱ ስታስብ ሀሳቡን ካልቀየረ በስተቀር እቤቴ እወስድሻለሁ ስላላት ያ በውስጧ የፈጠረባ ጉጉተና ደስታ ይመስላታል… .‹‹.እስኪ እሱ ቤት መሄድ እንዴት ነው እንደዚህ ሊያጓጓኝ የቻለው..?›እራሷን ጠየቀች፡፡
ከዚህ በፊት ዘመድ ካልሆነ በስተቀር ወንድ ልጅ ቤት ሄዳ ጣዕሙን ቀምሳ እንኳን አታውቅም…
.‹‹ወስዶ ሌላ ነገር ቢያደርገኝስ…?››.ሀሳቡን በማሰቧ እራሱ ሰውነቷ ተንቀጠቀጠባት……ማድረግ ቢፈልግ ስንት ቀን ሙሉ በውድቅት ለሊት ማንም በሌለበት እየተመላለሰችለት አይደል…? እርቃን ገላዋን ከገላው አጣብቃ ስትዋኝ አልነበር እንዴ?እንደዛ ማድረግ ቢፈልግ ማን ይከለክለው ነበር….?እንደዚህ ማሰቧ አጽናናት ፤ እና ፈገግ አለች፡፡
‹‹ ..ፈገግታሽ ያምራል››አላት ወንዝ ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለ ..ለካ ሳታስበው ደርሳ ወንዙ ጠርዝ አካባቢ ቆማ ነበር በሀሳብ ስትባዝን የነበረው፡፡
‹‹ደህና አደርክ››አለችው እንደመባነን ብላ
‹‹አዎ አድሬለሁ…ነይ ግቢ››አላት
‹‹ወዴት ነው የምገባው?››
‹‹ወደ ወንዙ ነዋ››
‹‹አልገባም …ቀጠሮ እኮ ነበረን ፤እረሳኸው እንዴ…?››
በሚያበሽቅ ና ተስፋ በሚያስቆርጥ የንግግር ቃና‹‹የምን ቀጠሮ?›› አላት ፡
ትንሿን ለንቦጯን ጥላ‹‹ተወው በቃ››አለችው፡፡
ፈገግ አለና‹‹..ኩሪፊያሽን እኮ በጣም ስለምወድልሽ ነው..እቤቴን ላሳይሽ አይደል ቀጠሯችን….?ነይ ግቢና አምስት ደቂቃ አብረን ዋኝተን እንሄዳለን..››
‹‹አምስት ደቂቃ ብቻ!!!››
‹‹አዎ.. አምስት ደቂቃ ብቻ››
‹‹..ተስማምታ ቀሚሷን አወለቀችና ደረቅ ቦታ አጣጥፋ በማስቀመጥ በፓንት ብቻ ዘላ እጠገቡ ቦጭረቅ አለች››..….አንጠልጥሎ አቀፋትና ይዞት ወደ ውሀ ውስጥ ሰመጠ …ከእቅፉ ለመውጣት ተንፈራገጠች… አልቻለችም፡፡ ይዟት ውስጥ ለውስጥ እየዋኘ ነው፡፡ ሳታስበው ከንፈሩን ከንፈሯ ላይ አጣበቀው..የሆነ በቃላት ልትገልፀው የማትችለው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ሞገድ ከጎረሰው ከንፈሯ ተነስቶ እላይ ጭንቅላቷ. ድረስ እንደገና ከዛው ከተጎረሰው ከንፈሯ ተነስቶ ወደታች እግር ጥፍሯ ድረስ በመሰራጨት አንዘፈዘፋት ….የምትዋኝ ሳይሆን የምትንሳፈፍ ነበር የመስላት… ለ5 ደቂቃ በእንደዛ አይነት ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ከዋኙ በኃላ የተደረመሰ ጉድጓድ ያለው የመሬት ስንጥቅ የወንዝ ወለል ላይ በአይኗ ገባ ….
‹‹አለየውም ይሆን ?››ብላ በማሰብ ልታስጠነቅቀው ፈልጋ ለመናገር ከንፈሯን ለማለቃቀቅ ብትጥርም አልቻለችም …ይዟት እያመራ ያለው ወደዛው አቅጣጫ ነው….የሚያስፈራ አይነት ጉድጓድ ነው …እንደውም አስፈሪ የአውሬ አፍ ይመስላል…ዳሩ ምንም ማድረግ ሳትችል ይባስ ብሎ ከንፈሩን ከከንፈሯ ሰውነቱን ከሰውነቷ እንዳጣበቀ በስንጥቁ መሬት አፉ ውስጥ ገባና ወደጥልቁ. ይዞት ጭልጥ አለ….
‹‹ወይኔ ልጅት …..ምን አይነት ተአምር ነው….?ምን አይነት ቀበጥ ልጅ ነኝ…?እንዴት ደፍሬ ነው ከዚህ ሰይጣን ጋር የተወዳጀሁት…?.መወዳጀቱንስ እሺ ልወዳጅ እንዴት የማያስብ አዕምሮ ቢኖረኝ ነው ቤትህን ካላሰየህኝ ብዬ ወጥሬ የያዝኩት…?›ስትል ግትልትል ጥያቄዎችን እራሷን ጠየቀች…መልስ መላሽ ግን አልነበረም .. ወደ ሲኦል ይዞት እየጠለቀ ያለ ነው የመሰላት…, ‹‹ግን ሲኦል የት ነው የሚገኘው››.…..? ከምድር በላይ ሰማይ ላይ ነው ወይስ ከምድር በታች ካለ ስምጥ ጨለማ ውስጥ….?አይ አሁን ይዞኝ እየሰመጠ ያለው ከምድር እንብርት ከሚገኝ ጨለማ ነው ..››በፍራቻ ተቀፍድዳ ነፍሷ ጭምር እየቃተች ቢሆንም እዕምሮዋ ግን በሀሳብ ግትልትል ከመብሰልሰል እራሷን መግታት አልቻለችም፡፡ አዎ ምንም እየታያት አይደለም‹‹….ደግሞ አንደርስም እንዴ…?›አለች ፡፡
..በቃ ሲኦል ውስጥ መቼስ ያለው የሚንቀለቀል እቶን እሳት ነው…ነፍስ አባቷ ብዙ ጊዜ ሲናገሩ ሰምታለች…አይ እሳት ብቻም አይደለም ሰውነትን የሚበጣጥስ ቀዝቃዛ በረዶም አለ ብለዋታል…‹‹ግን እቶን እሳት እና ቀዝቃዛ ግግር በረዶ በአንድ የሲኦል ካምፕ ውስጥ እንዴት መገኘት ይችላሉ…?ሁለቱ እርስ በርሳቸው አይጠፋፉም እንዴ…?››ሀሳቧ ለራሷ አስገረማት.‹‹ የእኔ ነገር አሁን ስለዚህ የማስብበት ሁኔታ ላይ ነኝ…?›› ቤተሰቦቾን እሬሳዋን እንኳን ሳያገኙት ቀጥታ በጎሮ በር ወደሲኦል መሄዷ በጣም ልብ ሰባሪ ገጠመኝ ነው የሆነባት…?ከሀሳብ ቅርቃር ውስጥ ሳትወጣ ከንፈሩን ከከንፈሯ ድንገት ሲያነሳ የተለየ አዲስ አይነት ከልብ የመነጠቅ አይነት ስሜት ተሰማት ፡፡
…አዎ እግሮቾ ለስለስ የሚል ነገር ላይ ቆመዋል…እጆቹ ከሰውነቷ ተላቀቁ .. ሰውነቱንም ከሰውነቷ አለያየው… ግን በጨለማ ደብዝዞ እና ጨፍና የነበሩትን አይኖቾን መግለጥ ፈራች…‹‹.ሲኦል ደርሰናል ማለት ነው..?››ስትል ጠየቀች.. ግን የእሳቱም ወላፈን እያቃጠለት አይደለም.. የበረዶው ቅዝቃዜውም ለሰውነቷ እየተሰማት አይደለም…በተቀራኒው ከገነት የሚመነጭ አይነት አየር በአፍንጫዋ እየሳበች ነው::እንደዛ መሆኑ ደግሞ ጥሩ ነገር እንዲሰማት እያደረገ ነው፡፡
‹‹ደርሰናል ግለጪ››የሚል ድምጽ ሰማች…
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
እለቱ እሁድ …ሰማይና ምድሩ ከመላቀቁ በፊት በሚባልበት የለሊቱ የጊዜ ክፍል ላይ ነው፡፡ ኦርቶዶክሶቹ ቤተሰቦቾ ተነስተው አምላካቸውን ለመማፀን ቅ/ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተያይዘው ግቢውን ለቀው እንደወጡ እሷም ተስፈንጥራ መኝታዋን ለቀቀችና እቤቱን በታናናሽ ወንድሞቾ ላይ ከውጭ መለስ አድርጋባቸው ግቢውን ለቃ ቁልቁለቱን በመንደርደር እንቅፍት እያላተማት ወደ ያዶት ሩጫዋን ቀጠለች..ይገርማል ጄሬካን እንዳልያዘች እንኳን ትዝ ያላት የወንዙን የለሊት ሿሿታ ድምጽ ለጆሮዋ ከደረሰ በኃላ ነበር፡፡
‹‹ወይ ጉዴ….ምን መሆኔ ነው …? እሱስ እንዴት ይታዘበኝ…?›ስትል በውስጧ እራሷን ታዘበች፡፡
እንደዛም ቢሆንም ግን እርምጃዋን አልጋታችም ….ቀጥታ ወደ ወንዙ አመራች…፡፡ በእለቱ የተለየ መንቀዥቀዥ፤ የተለየ መቀበጥበጥ.፤የተለየ መቁላላት 🤭 እየታየባት ነበር… ምክንያቱ ስታስብ ሀሳቡን ካልቀየረ በስተቀር እቤቴ እወስድሻለሁ ስላላት ያ በውስጧ የፈጠረባ ጉጉተና ደስታ ይመስላታል… .‹‹.እስኪ እሱ ቤት መሄድ እንዴት ነው እንደዚህ ሊያጓጓኝ የቻለው..?›እራሷን ጠየቀች፡፡
ከዚህ በፊት ዘመድ ካልሆነ በስተቀር ወንድ ልጅ ቤት ሄዳ ጣዕሙን ቀምሳ እንኳን አታውቅም…
.‹‹ወስዶ ሌላ ነገር ቢያደርገኝስ…?››.ሀሳቡን በማሰቧ እራሱ ሰውነቷ ተንቀጠቀጠባት……ማድረግ ቢፈልግ ስንት ቀን ሙሉ በውድቅት ለሊት ማንም በሌለበት እየተመላለሰችለት አይደል…? እርቃን ገላዋን ከገላው አጣብቃ ስትዋኝ አልነበር እንዴ?እንደዛ ማድረግ ቢፈልግ ማን ይከለክለው ነበር….?እንደዚህ ማሰቧ አጽናናት ፤ እና ፈገግ አለች፡፡
‹‹ ..ፈገግታሽ ያምራል››አላት ወንዝ ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለ ..ለካ ሳታስበው ደርሳ ወንዙ ጠርዝ አካባቢ ቆማ ነበር በሀሳብ ስትባዝን የነበረው፡፡
‹‹ደህና አደርክ››አለችው እንደመባነን ብላ
‹‹አዎ አድሬለሁ…ነይ ግቢ››አላት
‹‹ወዴት ነው የምገባው?››
‹‹ወደ ወንዙ ነዋ››
‹‹አልገባም …ቀጠሮ እኮ ነበረን ፤እረሳኸው እንዴ…?››
በሚያበሽቅ ና ተስፋ በሚያስቆርጥ የንግግር ቃና‹‹የምን ቀጠሮ?›› አላት ፡
ትንሿን ለንቦጯን ጥላ‹‹ተወው በቃ››አለችው፡፡
ፈገግ አለና‹‹..ኩሪፊያሽን እኮ በጣም ስለምወድልሽ ነው..እቤቴን ላሳይሽ አይደል ቀጠሯችን….?ነይ ግቢና አምስት ደቂቃ አብረን ዋኝተን እንሄዳለን..››
‹‹አምስት ደቂቃ ብቻ!!!››
‹‹አዎ.. አምስት ደቂቃ ብቻ››
‹‹..ተስማምታ ቀሚሷን አወለቀችና ደረቅ ቦታ አጣጥፋ በማስቀመጥ በፓንት ብቻ ዘላ እጠገቡ ቦጭረቅ አለች››..….አንጠልጥሎ አቀፋትና ይዞት ወደ ውሀ ውስጥ ሰመጠ …ከእቅፉ ለመውጣት ተንፈራገጠች… አልቻለችም፡፡ ይዟት ውስጥ ለውስጥ እየዋኘ ነው፡፡ ሳታስበው ከንፈሩን ከንፈሯ ላይ አጣበቀው..የሆነ በቃላት ልትገልፀው የማትችለው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ሞገድ ከጎረሰው ከንፈሯ ተነስቶ እላይ ጭንቅላቷ. ድረስ እንደገና ከዛው ከተጎረሰው ከንፈሯ ተነስቶ ወደታች እግር ጥፍሯ ድረስ በመሰራጨት አንዘፈዘፋት ….የምትዋኝ ሳይሆን የምትንሳፈፍ ነበር የመስላት… ለ5 ደቂቃ በእንደዛ አይነት ሁኔታ ውስጥ ለውስጥ ከዋኙ በኃላ የተደረመሰ ጉድጓድ ያለው የመሬት ስንጥቅ የወንዝ ወለል ላይ በአይኗ ገባ ….
‹‹አለየውም ይሆን ?››ብላ በማሰብ ልታስጠነቅቀው ፈልጋ ለመናገር ከንፈሯን ለማለቃቀቅ ብትጥርም አልቻለችም …ይዟት እያመራ ያለው ወደዛው አቅጣጫ ነው….የሚያስፈራ አይነት ጉድጓድ ነው …እንደውም አስፈሪ የአውሬ አፍ ይመስላል…ዳሩ ምንም ማድረግ ሳትችል ይባስ ብሎ ከንፈሩን ከከንፈሯ ሰውነቱን ከሰውነቷ እንዳጣበቀ በስንጥቁ መሬት አፉ ውስጥ ገባና ወደጥልቁ. ይዞት ጭልጥ አለ….
‹‹ወይኔ ልጅት …..ምን አይነት ተአምር ነው….?ምን አይነት ቀበጥ ልጅ ነኝ…?እንዴት ደፍሬ ነው ከዚህ ሰይጣን ጋር የተወዳጀሁት…?.መወዳጀቱንስ እሺ ልወዳጅ እንዴት የማያስብ አዕምሮ ቢኖረኝ ነው ቤትህን ካላሰየህኝ ብዬ ወጥሬ የያዝኩት…?›ስትል ግትልትል ጥያቄዎችን እራሷን ጠየቀች…መልስ መላሽ ግን አልነበረም .. ወደ ሲኦል ይዞት እየጠለቀ ያለ ነው የመሰላት…, ‹‹ግን ሲኦል የት ነው የሚገኘው››.…..? ከምድር በላይ ሰማይ ላይ ነው ወይስ ከምድር በታች ካለ ስምጥ ጨለማ ውስጥ….?አይ አሁን ይዞኝ እየሰመጠ ያለው ከምድር እንብርት ከሚገኝ ጨለማ ነው ..››በፍራቻ ተቀፍድዳ ነፍሷ ጭምር እየቃተች ቢሆንም እዕምሮዋ ግን በሀሳብ ግትልትል ከመብሰልሰል እራሷን መግታት አልቻለችም፡፡ አዎ ምንም እየታያት አይደለም‹‹….ደግሞ አንደርስም እንዴ…?›አለች ፡፡
..በቃ ሲኦል ውስጥ መቼስ ያለው የሚንቀለቀል እቶን እሳት ነው…ነፍስ አባቷ ብዙ ጊዜ ሲናገሩ ሰምታለች…አይ እሳት ብቻም አይደለም ሰውነትን የሚበጣጥስ ቀዝቃዛ በረዶም አለ ብለዋታል…‹‹ግን እቶን እሳት እና ቀዝቃዛ ግግር በረዶ በአንድ የሲኦል ካምፕ ውስጥ እንዴት መገኘት ይችላሉ…?ሁለቱ እርስ በርሳቸው አይጠፋፉም እንዴ…?››ሀሳቧ ለራሷ አስገረማት.‹‹ የእኔ ነገር አሁን ስለዚህ የማስብበት ሁኔታ ላይ ነኝ…?›› ቤተሰቦቾን እሬሳዋን እንኳን ሳያገኙት ቀጥታ በጎሮ በር ወደሲኦል መሄዷ በጣም ልብ ሰባሪ ገጠመኝ ነው የሆነባት…?ከሀሳብ ቅርቃር ውስጥ ሳትወጣ ከንፈሩን ከከንፈሯ ድንገት ሲያነሳ የተለየ አዲስ አይነት ከልብ የመነጠቅ አይነት ስሜት ተሰማት ፡፡
…አዎ እግሮቾ ለስለስ የሚል ነገር ላይ ቆመዋል…እጆቹ ከሰውነቷ ተላቀቁ .. ሰውነቱንም ከሰውነቷ አለያየው… ግን በጨለማ ደብዝዞ እና ጨፍና የነበሩትን አይኖቾን መግለጥ ፈራች…‹‹.ሲኦል ደርሰናል ማለት ነው..?››ስትል ጠየቀች.. ግን የእሳቱም ወላፈን እያቃጠለት አይደለም.. የበረዶው ቅዝቃዜውም ለሰውነቷ እየተሰማት አይደለም…በተቀራኒው ከገነት የሚመነጭ አይነት አየር በአፍንጫዋ እየሳበች ነው::እንደዛ መሆኑ ደግሞ ጥሩ ነገር እንዲሰማት እያደረገ ነው፡፡
‹‹ደርሰናል ግለጪ››የሚል ድምጽ ሰማች…
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ለታደሉ ጋብቻ ገነታዊ ደህንነት የተላበሰ የደስታ ቅፅር ይሆንላቸዋል ለሌላው ደግሞ በእቶን እሳት የታጠረ ሲኦላዊ የግዞት ቦታ ነው…፡፡
ከሠዓት በኋላ ወደ ማተሚያ ቤት መላክ ያለባቸውን የጋዜጣ ፅሁፎችን ለመጨረሻ ጊዜ ተመልክቶ ጨረሰና በድካም ስሜት ወደ ኋላው ተንጠራራ፡፡ለወትሮ ለአስራ ስድስት ሠዓት ያለዕረፍት ሲሠራ የድካም ስሜት የማይሠማው ሠውዬ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሁለት እና ሦስት ሰዓት ስራም ያዝለው ጀምሯል፡፡
‹‹ኢንጅነር ሠሎሞን ዛሬ ደግሞ ምነው ይበልጥ አጠርክ?›› ድንገት በራፉን ከፍቶ ወደ ቢሮው እየገባ ያለውን ጓደኛውን በተረብ ተቀበለው፡፡
‹‹ዓይንህ ነው››
‹‹አይመስለኝም፡፡ ኧረ ይሄንን ቦርጭ ቀንስ፡፡ የድሮዎቹ ኢንጅነሮች ኪሳቸውን ብቻ ነበር የሚቆዝሩት፤ያሁኖቹ ደግሞ ሆዳችሁንም ሳይቀር በስብ ትቆዝራላችሁ፡፡››
‹‹ባክህ አትጨቅጭቀኝ፡፡›› በማለት ወንበር ስቦ ፊት ለፊቱ ተቀመጠ ፡፡
‹‹ፕሮጀክትህን ለማየት ባህርዳር የሄድክ መስሎኝ ነበር?››
ቀረሁ ባክህ ከሶስት ቀን በኋላ የልጆቼ ልደት ነው፤ ዘንግቼው ነበር ሄዳለሁ ያልኩህ፡፡››
‹‹ኦ ..! መንታዎቹ ስምንተኛ ዓመታቸው መሆኑ ነው? >>
‹‹አዋ! ደረሱልኝ፡፡ ብቻ ለአቅመ ሄዋን ሲደርሱ እንደአንተ አይነቶቹን አዳሞች ከምድር ሚጠራርግልኝ ነገር ቢፈጠር ፍቃዴ ነው፡፡››
‹‹እንዴት ባክህ?›› ሁሴን በገረሜታና በፈገግታ ጠየቀው፡፡
‹‹ምን እንዴት ትለኛለህ...በሄዋኖች ላይ እየተጫወትክ፤ ደግሞ በቀደም ምንድነው የሠራኸው?››
«...ምን ሰራው?»
‹‹ሁለቱን ሴቶች በአንድ ላይ ጠርተህ ልታቧቅሳቸው ነው ወይስ ልታሳስማቸው?››
‹‹ኧኧ .. ማን ነገረህ ደግሞ?››
‹‹ኤደን ደውላልኝ ተገናኝተን ነበር፡፡ የእሷ ልጅ እምባ ከፀረ አርያም የደረሠ ቀን ምን እንደሚውጥህ እኔ አላውቅም፡፡ ቆይ ምን እያስነካሀቸው ነው እንደሙጫ ተጣብቀው እኝኝ የሚሉብህ?›› ግርምት በተቀላቀለ ስሜት ነው የሚጠይቀው፡፡
‹‹እሱን እራሳቸውን ብትጠይቃቸው አይሻልም ..ቆይ ምን ሆንኩ አለችህ?››
‹‹እሷማ በእሱ ያልሆንኩት ነገር የለም ነው የምትለው...እኔም እውነቷን ነው እላለሁ፡፡ እንደውም ምን እንዳልኳት ታውቃለህ፡፡ይሄን ያህል ከተንገሸገሺበት ተይው፤ እኔም በሚስቴ ተማርሪያለሁ፤ ስለዚህ ልፍታትና እንጋባ፤ሁለት ብሶተኞች ቢገናኙ የደስታ ኑሮ ሊገጥማቸው ይችል ይሆናል፡፡ ››አልኳት፡፡
‹‹ድንቅ መፍትሄ ነው፤እንደተስማማች እገምታለሁ፡፡››
‹‹ምን ትስማማለች፡፡ እኔ በቁም ነገር ችግሬን ሳዋይህ አንተ ታሾፋለህ አለችኝ፡፡ አልተረዳችኝም እንጂ እኔስ ከአንጀቴ ነበር፡፡ ያቺን የመሠለች መልዐክ ከእንዳንተ አይነቱ ነጂስ ባድናት እርግጠኛ ነኝ ከፃድቃን ተርታ ያሰልፈኛል፤እኔም ከዛች መሠሪ ሚስት ተብዬ እገላገል ነበር፡፡››
‹‹መስሎሀል... ያህቺ አሁን መልዐክ የመሠለችህ ወደ ትዳር ይዘሀት ስትዘልቅ የባሰች ሠይጣን ልትሆን ትችላለች፡፡
ከማግባትህ በፊት ለየውብዳር እንዴት
ትንሰፈሰፍላት እንደነበር ዘነጋኸው? የፍቅር
ግንኙነትና የጋብቻ ጥምረት ፍፁም የተለያዩ ሂደቶች ናቸው፡፡አየህ በፍቅረኝነት ሃያ ሠላሳ ዓመት ጣፋጭ የስምምነት ህይወት መኖር
እምብዛም የሚከብዱ አይደለም፡፡ ምክንያቱም
የተወሰነ ክፍተት .. መፈናፈኛ ቦታ .. ነፃነት
እንዲሁም እኔ እና እሱ የሚል ልዩነት አለና፡፡
በጋብቻ ውስጥ ግን ከተወሰኑ ዓመታት በላይ
ፍቅርን ከእነ ጣዕሙና ወዙ ማቆየት ለጥቂቶች ብቻ ነው የሚቻለው፡፡ እኔ እና እሷ የሚለውን ቃል ፍፁም ደምስሶ እኛ በሚለው ቃል
ለመተካት ጥረት ይደረጋል፡፡ ዳሩ ግን ሃያ ሰላሳ ዓመት በተለያየ የኑሮ ዘየ በተለያየ ቤተሰብ ውስጥ የኖሩ ሁለት የተለያዩ ግለሰቦች አንድ
ይሆናሉ ብሎ ማሰብ በራሱ እብደት ነው፡፡
የፍቅር ተቋም ከጋብቻ ተቋም ፍፁም የተለየ
ነው፡፡አየህ አብዛኞቹ በምድራችን የተከሰቱ
የፍቅር ታሪኮች (ልብ ወለዶቹ ሳይቀሩ)
የሚያረጋገረጡት ይህንን ሀቅ ነው፡፡
የሼክስፒሮቹ ሮሚዮና ጁልዮት፤ የአዲስ አለማየሁ በዛብህና ሠብለ ወንጌል ሁሉም በመከራ እንጂ በጋብቻ አልተፈተኑም፡፡ምን ' አልባት ተሳክቶላቸው ከዛ ሁሉ የህይወት ፈተና በኋላ ወደ ጋብቻ አምርተው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ታሪካቸው ሌላ መልክ ይይዝ ነበር፤በፍቺም ሊጠናቀቅ ይችል ነበር፡፡ፈተና ለፍቅረኞች ብርታት ነው፣ ወኔ ነው፣አቅም ነው፡፡ በተለይ ሁለቱን ለመነጣጠል የሚደረግን ማንኛውንም አሻጥርን ለመበጣጠስ ያላቸው እምቅ ጉልበት ከኒውክሌር ይስተካከላል፡፡ ጉልበታቸው የሚመነጨው ከፍቅራቸው ብቻ ሳይሆን ከመከልከላቸው ውስጥ ነው፡፡ መከልከል ከሠው ልጅ የስነ ልቦና ታሪክ ጋር ትልቅ ትስስር አለው፡፡››
‹‹ገባኝ፡፡ ያንተዋ ኤደን ቢጤ ማለት ነው፡፡ ይሄኔ ላግባሽ እያልክ ብትለምናት ኖሮ ጉዳዩ ተቃራኒ ይሆን ነበር፡፡›› ሠሎሞን ነው ቦርጩን እያሻሸ በመሀከል ገብቶ ሀሳብን የሠነዘረው፡፡
ሁሴን ንግግሩን ቀጠለ ‹‹በተወሰነ መልኩ ትክክል ነህ፡፡ የሠው ልጅ የተከለከለውን ነገር
ለመጨበጥ ቀን ከሌት ይጥራል፡፡ እስኪሳካለትም እረፍት አልባ ይሆናል፡፡ ስለ ግብ አይጨነቅም፡፡ የተከለከለውን በእጁ ካላስገባ ደካማ ነኝ ብሎ ያስባል እንጂ ነገሩ ለእኔ ምን ያህል ያስፈልገኛል፤ ከውስጣዊ ፍላጎቴስ ጋር ምን ያህል ትስስር አለው? ብሎ መጨነቅ ብዙ አይስተዋልበትም፡፡ የአብዛኞቻችን የፍቅር ታሪክም ይህን መሠል ነው፡፡የፍቅር ጉዞ ይጀመራል... በጉዞ ውስጥ እንቅፋት ይደነቀራል.... በዚህ ወቅት ፍላጎት በእጥፍ ይጨምራል፡፡ እንቅፋቱን ለማስወገድ የዓመታት ፍልሚያ ይጀምራል፡፡ በፍልሚያው ሜዳ ላይ የሚከፈለው የመስዋዕትነት መጠን የፍቅር መጠን መለኪያም ተደርጎ ይወሠዳል፡፡ የታገለ ማሸነፉ ወይም መሸነፉ አይቀርምና በመጨረሻ በስኬት ከተጠናቀቀ ቀጥታ ፍቅር ወደ ጋብቻ ይሸጋገራል፡፡ክፍተት የሌለበት ውህደት፤ አንዱ የሌላው የግል ንብረት ይሆናል፡፡ታዲያ ሲሰነባብት ጀብዱ የለ...ትግል የለ...ግራ መጋባት ይከሰታል፡፡ከውጭ የሚታገላቸው ሲያጡ ፊታቸውን ወደ ጋብቻ
ተጣማሪያቸው ያዞራሉ፤እርስ በርስ ፍትጊያ ይጀመራል…፡፡ ውጫዊ ትግል በውስጣዊ ጭቅጭቅና አንባጓሮ ይተካል፡፡ እሱ እሷ ላይ ይጮኸል…እሷም እሱ ላይ ታንቧርቃለች፡፡ በስተመጨረሻም ውጤቱ ሁለት ይሆናል፤ አንድም የትግሉ ውጤት በመሸናነፍ ይጠናቀቅና ‹ጨዋታ ፈረሠ ዳቦ ተቆረሠ› ተብሎ ትዳሩ ይፈርሳል፤ሁለተኛው ደግሞ ለይሉኝታ ሲባል .. በመሀከል ለተፈጠሩ ልጆች ሲባል ወይም በጋራ ላፈሩት ቁሳዊ ሀብት ሲባል ጋብቻው የዕድሜ ልክ የፍልሚያ ሜዳ ሆኖ ይቀጥላል፡፡
ጥቂት በነፃነት ላይ የተመሠረተ ፍቅር ግን በእጮኝነትም ሆነ በጋብቻ ጊዜ ተመሳሳይ አንድምታ ሊኖረው ይችላል፡፡ከተለያዩ ሁለት ቤተሰብ የመጣን ሁለት የተለያየን ሠዎች ስለሆንን በሁሉ ነገር ላይ መስማማት አይጠበቅብንም፤በሚያስማማን ነገር ላይ እንስማማለን፤አንዳችን የሌላችንን የተለየ ፍላጎትም እናከብራለን፡፡›› በማለት ተግባብተው ከፍቅር ዘለው ወደ ጋብቻ የዘለቁ
ጥቂቶች ችግር አልባ የሆነ ጣፋጭና ምቹ ህይወት ለመምራት ይታደላሉ፡፡ >>
‹‹ፍልስፍና መዘባረቅና ህይወትን ቀጥታ መኖር ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ምን አለበት የእኔን ትዳር ለሦስት ወር ብትሞክረው እሳቱ እንዴት እንደሚያቃጥል ትረዳልኝ ነበር፡፡››
‹‹ያንተን ሳይሆን የራሴኑ እሞክረዋለሁ፤ደራሲዋን ሳገባ፡፡ ግን እስቲ ንገረኝ አሁን የውብዳር ፍታኝ ብትልህ ትፈታታለህ?»
<<እኔንጃ>>
‹‹እንዴት እኔ እንጃ?››
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ለታደሉ ጋብቻ ገነታዊ ደህንነት የተላበሰ የደስታ ቅፅር ይሆንላቸዋል ለሌላው ደግሞ በእቶን እሳት የታጠረ ሲኦላዊ የግዞት ቦታ ነው…፡፡
ከሠዓት በኋላ ወደ ማተሚያ ቤት መላክ ያለባቸውን የጋዜጣ ፅሁፎችን ለመጨረሻ ጊዜ ተመልክቶ ጨረሰና በድካም ስሜት ወደ ኋላው ተንጠራራ፡፡ለወትሮ ለአስራ ስድስት ሠዓት ያለዕረፍት ሲሠራ የድካም ስሜት የማይሠማው ሠውዬ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሁለት እና ሦስት ሰዓት ስራም ያዝለው ጀምሯል፡፡
‹‹ኢንጅነር ሠሎሞን ዛሬ ደግሞ ምነው ይበልጥ አጠርክ?›› ድንገት በራፉን ከፍቶ ወደ ቢሮው እየገባ ያለውን ጓደኛውን በተረብ ተቀበለው፡፡
‹‹ዓይንህ ነው››
‹‹አይመስለኝም፡፡ ኧረ ይሄንን ቦርጭ ቀንስ፡፡ የድሮዎቹ ኢንጅነሮች ኪሳቸውን ብቻ ነበር የሚቆዝሩት፤ያሁኖቹ ደግሞ ሆዳችሁንም ሳይቀር በስብ ትቆዝራላችሁ፡፡››
‹‹ባክህ አትጨቅጭቀኝ፡፡›› በማለት ወንበር ስቦ ፊት ለፊቱ ተቀመጠ ፡፡
‹‹ፕሮጀክትህን ለማየት ባህርዳር የሄድክ መስሎኝ ነበር?››
ቀረሁ ባክህ ከሶስት ቀን በኋላ የልጆቼ ልደት ነው፤ ዘንግቼው ነበር ሄዳለሁ ያልኩህ፡፡››
‹‹ኦ ..! መንታዎቹ ስምንተኛ ዓመታቸው መሆኑ ነው? >>
‹‹አዋ! ደረሱልኝ፡፡ ብቻ ለአቅመ ሄዋን ሲደርሱ እንደአንተ አይነቶቹን አዳሞች ከምድር ሚጠራርግልኝ ነገር ቢፈጠር ፍቃዴ ነው፡፡››
‹‹እንዴት ባክህ?›› ሁሴን በገረሜታና በፈገግታ ጠየቀው፡፡
‹‹ምን እንዴት ትለኛለህ...በሄዋኖች ላይ እየተጫወትክ፤ ደግሞ በቀደም ምንድነው የሠራኸው?››
«...ምን ሰራው?»
‹‹ሁለቱን ሴቶች በአንድ ላይ ጠርተህ ልታቧቅሳቸው ነው ወይስ ልታሳስማቸው?››
‹‹ኧኧ .. ማን ነገረህ ደግሞ?››
‹‹ኤደን ደውላልኝ ተገናኝተን ነበር፡፡ የእሷ ልጅ እምባ ከፀረ አርያም የደረሠ ቀን ምን እንደሚውጥህ እኔ አላውቅም፡፡ ቆይ ምን እያስነካሀቸው ነው እንደሙጫ ተጣብቀው እኝኝ የሚሉብህ?›› ግርምት በተቀላቀለ ስሜት ነው የሚጠይቀው፡፡
‹‹እሱን እራሳቸውን ብትጠይቃቸው አይሻልም ..ቆይ ምን ሆንኩ አለችህ?››
‹‹እሷማ በእሱ ያልሆንኩት ነገር የለም ነው የምትለው...እኔም እውነቷን ነው እላለሁ፡፡ እንደውም ምን እንዳልኳት ታውቃለህ፡፡ይሄን ያህል ከተንገሸገሺበት ተይው፤ እኔም በሚስቴ ተማርሪያለሁ፤ ስለዚህ ልፍታትና እንጋባ፤ሁለት ብሶተኞች ቢገናኙ የደስታ ኑሮ ሊገጥማቸው ይችል ይሆናል፡፡ ››አልኳት፡፡
‹‹ድንቅ መፍትሄ ነው፤እንደተስማማች እገምታለሁ፡፡››
‹‹ምን ትስማማለች፡፡ እኔ በቁም ነገር ችግሬን ሳዋይህ አንተ ታሾፋለህ አለችኝ፡፡ አልተረዳችኝም እንጂ እኔስ ከአንጀቴ ነበር፡፡ ያቺን የመሠለች መልዐክ ከእንዳንተ አይነቱ ነጂስ ባድናት እርግጠኛ ነኝ ከፃድቃን ተርታ ያሰልፈኛል፤እኔም ከዛች መሠሪ ሚስት ተብዬ እገላገል ነበር፡፡››
‹‹መስሎሀል... ያህቺ አሁን መልዐክ የመሠለችህ ወደ ትዳር ይዘሀት ስትዘልቅ የባሰች ሠይጣን ልትሆን ትችላለች፡፡
ከማግባትህ በፊት ለየውብዳር እንዴት
ትንሰፈሰፍላት እንደነበር ዘነጋኸው? የፍቅር
ግንኙነትና የጋብቻ ጥምረት ፍፁም የተለያዩ ሂደቶች ናቸው፡፡አየህ በፍቅረኝነት ሃያ ሠላሳ ዓመት ጣፋጭ የስምምነት ህይወት መኖር
እምብዛም የሚከብዱ አይደለም፡፡ ምክንያቱም
የተወሰነ ክፍተት .. መፈናፈኛ ቦታ .. ነፃነት
እንዲሁም እኔ እና እሱ የሚል ልዩነት አለና፡፡
በጋብቻ ውስጥ ግን ከተወሰኑ ዓመታት በላይ
ፍቅርን ከእነ ጣዕሙና ወዙ ማቆየት ለጥቂቶች ብቻ ነው የሚቻለው፡፡ እኔ እና እሷ የሚለውን ቃል ፍፁም ደምስሶ እኛ በሚለው ቃል
ለመተካት ጥረት ይደረጋል፡፡ ዳሩ ግን ሃያ ሰላሳ ዓመት በተለያየ የኑሮ ዘየ በተለያየ ቤተሰብ ውስጥ የኖሩ ሁለት የተለያዩ ግለሰቦች አንድ
ይሆናሉ ብሎ ማሰብ በራሱ እብደት ነው፡፡
የፍቅር ተቋም ከጋብቻ ተቋም ፍፁም የተለየ
ነው፡፡አየህ አብዛኞቹ በምድራችን የተከሰቱ
የፍቅር ታሪኮች (ልብ ወለዶቹ ሳይቀሩ)
የሚያረጋገረጡት ይህንን ሀቅ ነው፡፡
የሼክስፒሮቹ ሮሚዮና ጁልዮት፤ የአዲስ አለማየሁ በዛብህና ሠብለ ወንጌል ሁሉም በመከራ እንጂ በጋብቻ አልተፈተኑም፡፡ምን ' አልባት ተሳክቶላቸው ከዛ ሁሉ የህይወት ፈተና በኋላ ወደ ጋብቻ አምርተው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ታሪካቸው ሌላ መልክ ይይዝ ነበር፤በፍቺም ሊጠናቀቅ ይችል ነበር፡፡ፈተና ለፍቅረኞች ብርታት ነው፣ ወኔ ነው፣አቅም ነው፡፡ በተለይ ሁለቱን ለመነጣጠል የሚደረግን ማንኛውንም አሻጥርን ለመበጣጠስ ያላቸው እምቅ ጉልበት ከኒውክሌር ይስተካከላል፡፡ ጉልበታቸው የሚመነጨው ከፍቅራቸው ብቻ ሳይሆን ከመከልከላቸው ውስጥ ነው፡፡ መከልከል ከሠው ልጅ የስነ ልቦና ታሪክ ጋር ትልቅ ትስስር አለው፡፡››
‹‹ገባኝ፡፡ ያንተዋ ኤደን ቢጤ ማለት ነው፡፡ ይሄኔ ላግባሽ እያልክ ብትለምናት ኖሮ ጉዳዩ ተቃራኒ ይሆን ነበር፡፡›› ሠሎሞን ነው ቦርጩን እያሻሸ በመሀከል ገብቶ ሀሳብን የሠነዘረው፡፡
ሁሴን ንግግሩን ቀጠለ ‹‹በተወሰነ መልኩ ትክክል ነህ፡፡ የሠው ልጅ የተከለከለውን ነገር
ለመጨበጥ ቀን ከሌት ይጥራል፡፡ እስኪሳካለትም እረፍት አልባ ይሆናል፡፡ ስለ ግብ አይጨነቅም፡፡ የተከለከለውን በእጁ ካላስገባ ደካማ ነኝ ብሎ ያስባል እንጂ ነገሩ ለእኔ ምን ያህል ያስፈልገኛል፤ ከውስጣዊ ፍላጎቴስ ጋር ምን ያህል ትስስር አለው? ብሎ መጨነቅ ብዙ አይስተዋልበትም፡፡ የአብዛኞቻችን የፍቅር ታሪክም ይህን መሠል ነው፡፡የፍቅር ጉዞ ይጀመራል... በጉዞ ውስጥ እንቅፋት ይደነቀራል.... በዚህ ወቅት ፍላጎት በእጥፍ ይጨምራል፡፡ እንቅፋቱን ለማስወገድ የዓመታት ፍልሚያ ይጀምራል፡፡ በፍልሚያው ሜዳ ላይ የሚከፈለው የመስዋዕትነት መጠን የፍቅር መጠን መለኪያም ተደርጎ ይወሠዳል፡፡ የታገለ ማሸነፉ ወይም መሸነፉ አይቀርምና በመጨረሻ በስኬት ከተጠናቀቀ ቀጥታ ፍቅር ወደ ጋብቻ ይሸጋገራል፡፡ክፍተት የሌለበት ውህደት፤ አንዱ የሌላው የግል ንብረት ይሆናል፡፡ታዲያ ሲሰነባብት ጀብዱ የለ...ትግል የለ...ግራ መጋባት ይከሰታል፡፡ከውጭ የሚታገላቸው ሲያጡ ፊታቸውን ወደ ጋብቻ
ተጣማሪያቸው ያዞራሉ፤እርስ በርስ ፍትጊያ ይጀመራል…፡፡ ውጫዊ ትግል በውስጣዊ ጭቅጭቅና አንባጓሮ ይተካል፡፡ እሱ እሷ ላይ ይጮኸል…እሷም እሱ ላይ ታንቧርቃለች፡፡ በስተመጨረሻም ውጤቱ ሁለት ይሆናል፤ አንድም የትግሉ ውጤት በመሸናነፍ ይጠናቀቅና ‹ጨዋታ ፈረሠ ዳቦ ተቆረሠ› ተብሎ ትዳሩ ይፈርሳል፤ሁለተኛው ደግሞ ለይሉኝታ ሲባል .. በመሀከል ለተፈጠሩ ልጆች ሲባል ወይም በጋራ ላፈሩት ቁሳዊ ሀብት ሲባል ጋብቻው የዕድሜ ልክ የፍልሚያ ሜዳ ሆኖ ይቀጥላል፡፡
ጥቂት በነፃነት ላይ የተመሠረተ ፍቅር ግን በእጮኝነትም ሆነ በጋብቻ ጊዜ ተመሳሳይ አንድምታ ሊኖረው ይችላል፡፡ከተለያዩ ሁለት ቤተሰብ የመጣን ሁለት የተለያየን ሠዎች ስለሆንን በሁሉ ነገር ላይ መስማማት አይጠበቅብንም፤በሚያስማማን ነገር ላይ እንስማማለን፤አንዳችን የሌላችንን የተለየ ፍላጎትም እናከብራለን፡፡›› በማለት ተግባብተው ከፍቅር ዘለው ወደ ጋብቻ የዘለቁ
ጥቂቶች ችግር አልባ የሆነ ጣፋጭና ምቹ ህይወት ለመምራት ይታደላሉ፡፡ >>
‹‹ፍልስፍና መዘባረቅና ህይወትን ቀጥታ መኖር ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ምን አለበት የእኔን ትዳር ለሦስት ወር ብትሞክረው እሳቱ እንዴት እንደሚያቃጥል ትረዳልኝ ነበር፡፡››
‹‹ያንተን ሳይሆን የራሴኑ እሞክረዋለሁ፤ደራሲዋን ሳገባ፡፡ ግን እስቲ ንገረኝ አሁን የውብዳር ፍታኝ ብትልህ ትፈታታለህ?»
<<እኔንጃ>>
‹‹እንዴት እኔ እንጃ?››
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ _ዋቤ
እንደምንም ራሷን ተቆጣጥራ ያዘዛትን መድሀኒት በስርዓቱ ተጠቅማ በቀጠራት ቀን ከሳምንት በኋላ በሰዓቱ ሄደች።እንደደረሰች በሞቀ ፈገግታና ጠበቅ ባለ ሠላምታ ተቀበላትና።
"ቁርስ በልተሻል?›› ሲል ጠየቃት፤ግራገባት፡፡ አሰበች ቁርስ አልበላችም
..ጭርሱኑም ትዝ አላላት።ሳትመልስለት የለበሰውን ነጭ ጋዎን አውልቆ መስቀያው ላይ እያንጠለጠለ
"ጥሩ እኔም አልበላሁም...ወጣ ብለን እንብላ"አላትና ወደ መውጫው መራመድ ሲጀምር ቀድማው ከክፍሉ ወጣች፡፡ቆለፈውና ጎን ለጎን እየተራመዱ መኪናውን ወዳቆመበት ቦታ እየመራ ወሰዳት ፡፡ጋቢናውን ከፈተና ካስገባት በኋላ እሱ ዞሮ ገባና አንቀሳቀሰው… ሆስፒታሉን ለቀው ወጡና አስር ደቂቃ ያህል ከተጓዙ በኋላ የመናፈሻ ድባብ ያለው አሪፍ ሆቴል ይዟት ገባ።ቁርስ እዛው በሉ…ማኪያቶ እየጠጡ ወሬ ጀመሩ።
"ሳምንቱ ጥሩ አለፈ አይደል?"
"ምንም አይል?"
"እንዴት ምንም አይል... አመመሽ እንዴ ...ደውይልኝ ብዬሽ ነበር?››
"አይ ያን ያህል አላመመኝም..ግን ያው ወጣ ገባ ነበር"
"ያው እንዲህ አይነት ህመም በፍጥነት የሚወገድ አይደለም.. የረጅም ጊዜ ክትትልና ትዕግስት ይጠይቃል።በተለይ ያንቺ ጥረት ወሳኝነት አለው፡፡
ምክንያቱም ከበሽታው እንድታገግሚ ለማድረግ የሚያግዙሽ ነገሮች ምን ምን እደሆኑ በዝርዝር ብታውቂያቸውም በሽታው ግን በራሱ ከአንቺ በተቃርኖ ስለሚቆም ተግባራዊ ማድረጉ ፈተና ነው››
‹‹አልገባኝም››
‹‹በቀላሉ ላስረዳሽ… ለምሳሌ ጨጓራ በሽታ ያለበት ሰውን መድሀኒት ትሰጪውና ከዚህና ከዚያ አይነት ምግቦች ተጠበቅ ብለሽ ምክር ብትሰጪው ትዛዙን ለመተግበር የምግብ አምሮቱን መገደብ ብቻ ነው የሚጠበቅበት፤ ስለዚህ በቀላሉ ይከውነዋል፡፡ እንደአንቺ አይነት ችግር ያለበት ሰው ግን ለምሳሌ ጠዋት እንደተነሳሸ አልጋሽን አንጥፊ ብትባይ እሺ አነጥፋለሁ ልትይኝ ትችያለሽ፡፡ግን በተጫጫነሽ ቀን እንኳን ተነስቶ አልጋ ማንጠፍ ይቅርና ..አንሶላውንም ከፊትሽ ላይ ማንሳት ላትችይ ትችያለሽ. .ምክንያቱም ነገሮችን እንድትከውኚ የሚያዘው አእምሮሽ ነው…ችግር የተፈጠረው ዋና ማዘዣ ጣቢያው ላይ በመሆኑ ነገሮች ሁሉ ቀላል አይሆኑም ፡፡እርግጥ በጣም ጥሩ ነገር አሁን ባለው ሁኔታ አንቺ አስቸጋሪው ደረጃ ላይ አልደረስሽም…እንደምንም ተረባርበን ወደኋላ መመለስና ሁሉን ነገር ማስተካከል አለብን፣አሁን ካለሽበት አንድ ስቴፕ ወደፊት ከሄደ ግን ከባድ ነው የሚሆንብን….ለዚህ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርገሽ በከፍተኛ ትእግስት ጤናሽ ላይ ብቻ ማተኮር እንዳለብሽ ከማስጠንቂያ ጋር የምነግርሽ፡፡
"እኔ ደግሞ ትዕግስት ነው የሌለኝ....በቃ ምን ለማግኘት ነው ይሄንን ሁሉ ስቃይ ታግሼ ለመኖር የምጥረው? የሚለው መልስ ያላገኘሁለት ጥያቄ ነው።›
‹‹ግድ የለም፤ መጀመሪያ ካለሽበት የተጨናነቀ ህይወት ራስሽን አላቂና ዘና ባለ መንፈስ ከዛ በኋላ የምትፈልጊውን ሞት ትሞቺያለሽ››
‹‹አይ ዶክተር እየቀለድክብኝ ነው አይደል?››
‹‹አይ እየቀለድኩ አይደለም..ለመሆኑ ስራ እረፍት ላይ ነሽ አይደል?"
"አዎ እረፍት ወስጄያለሁ ..››
‹‹...ምን ያህል?"
‹‹አንድ ወር...ግን ከዛም በኋላ የምመለስ አይመስለኝም ።››
‹‹ሳባ ...ኑሮ አያሳስብሽም አይደል..?.ማለቴ ፋይናንሺያል?"
"ለመጪው መቶ አመት በዚህ ምድር ላይ ብንኖር ገንዘብ የሚቸግረኝ አይመስለኝም።››
"ጥሩ አሁን ወደሆስፒታል እንመለስና በቀደም ካቆምንበት እንቀጥል፤›› አላትና ተያይዘው ወደሆስፒታል ሄዱ።ለአንድ ሰዓት ያህል ካወሩ በኋላ ተጨማሪ አንድ ኪኒን አዘዘላትና ሳምንት በተመሳሳይ ቀን እንዲገናኙ ቀጠሮ በመስጠት አሰናበታት።ስትመጣ ከነበረችበት የበለጠ ተደብራ ነበር የተመለሠችው።ይሄ ሳምንት እየጠበቁ እሱ ጋር መመላለስ ብዙም ምቾት እየሠጣት አይደለም። መኪናዋን እየነዳች ወደቤቷ እየተጓዘች ሳለ ስልኳ ጠራ ...አሁን የያዘችውን ቁጥር በጣም ጥቂት የራሴ የምትላቸው ሰዎች ናቸው የሚያውቁት።ከነዛ ውስጥ ማን እንደደወለላት ለማወቅ በመጓጓት በአንድ እጇ መሪውን እንደያዘች በሌላ እጇ ወደኪሷ ገባችና ስልኩን አወጣች የደዋዩን ማንነት ስታይ ደነገጠች
...መኪናውን ወደዳር አቆመችና አነሳችው ።
"ሄሎ ራጂ"የ12 አመትና የ5ተኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ብቸኛና ተወዳጅ ታናሽ ወንድሟ ነው የደወለላት።እሱን እንኳን ደውላ ካናገረችው አንድ ወር ሊሞላት ነው።‹‹ጨርቄን ጥዬ አልሄድኩም እንጂ እኔማ በትክክል አብጄያለሁ›› ስትል በውስጧ አሰበች።ከእዛኛው ጫፍ ወንድሟ እያወራ ነው።
‹‹እህቴ. ምነው ጠፋሽብን...?ብዙ ጊዜ ስንደውል ስልክሽ አይሰራም››ቅሬታውን አሰማ፡፡
‹‹የእኔ ማር ደህና ነኝ..ትንሽ ስራ ስላጨናነቀኝ ነው..ለመሆኑ እናትህ ደህና ነች››
ከራጂ ጋር በአባት እንጂ በእናት አይገናኙም።ግን የራጅ እናት ለሳባ የእንጀራ እናቷ ብቻ ሳትሆን የልጅነት አብሮ አደግ ጓደኛዋ ጭምር ስለሆነች ቀረቤታቸው ዘመናት ያስቆጠረና የተለየ አይነት ነው።
‹‹እማዬማ...ደህና ነች ማለት ይከብዳል?››
ሳባ ደነገጠች"እንዴ ምን ሆነች...? አመማት እንዴ?››
‹‹እኔ እንጃ እህቴ?.ካንቺ ጋር ተጣልታቹሀል እንዴ?››
‹‹ማንና ማን.. እኔና ስንድ? የት ተገናኝተን...ይሄን ወሬ ከየት አመጣኸው?››
‹‹እህቴ ባትቀየመኝ ኖሮ እንዲህ አትረሳኝም ነበር...አንድ ልጄን አስቀይሜ የአባቷ መንፈስስ እንዴት ይታዘበኛል? እያለች ቀኑን ሙሉ ስታለቅስ ነው የምትውለው.. አይኗ እንዳይጠፋ ፈርቼ ነው የደወልኩልሽ››
ሳባ ጭንቅላቷ ላይ ብው ብሎ የሚነድ እሳት የተነሰነሰባት መሰላት‹‹የእኔ ማር...እናትህ ተሳስታለች...እሷ መቼም እኔን ልታስቀይመኝ አትችልም... ደግሞም በሆነ ነገር ብቀየምስ በግልፅ እንዲህ አድርገሽኛል እላለሁ እንጂ እንዴት እቀየማለሁ፤ ከአንተና ከእሷ ውጭ ሌላ ቤተሠብ አለኝ እንዴ?››
‹‹እሱማ የለሽም...ግን?››
‹‹ግን ምን?››
‹‹እኔ እንጃ ባትቀየሚ.ዛሬ እኛ ጋ ትመጪ ነበራ...››
‹‹የት አሰላ?››
‹‹አዎ ››
ብዥ አለባት ...መድሀኒት ስትወስድ የሚሰማትን የመደንዘዝ አይነት ስሜት ይሰማት ጀመረ..፡፡
‹‹ዛሬ ለምን?››
‹‹ነገ የአባዬ የሰባት አመት መታሰቢያው አይደለ እንዴ....?ባትቀየመኝ በአባቷ መታሰቢያ ቀን ከቤቷ አትቀርም ነበር ብላ እኮ ነው የምታለቅሰው..››
‹‹ራጂ ቆንጆ...አሁን መኪና እየነዳሁ መጥፎ ቦታ ነኝ ያለሁት...ማታ ልደውልልህ››
‹‹እሺ እህቴ እወድሻለሁ፡፡››
‹‹እኔም እወድሀለሁ የእኔ ማር፡፡››ስልኩን ዘጋችና ..መኪናዋን አንቀሳቀሰች ...ወደአስፓልት መሀል ካስገባች በኃላ መጠምዘዣ እስክታገኝ ወደፊት ነዳች፡፡ ከዛ አቅጣጫዋን ለውጣ መንዳት ጀመረች.፡፡
💫ይቀጥላል💫
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ _ዋቤ
እንደምንም ራሷን ተቆጣጥራ ያዘዛትን መድሀኒት በስርዓቱ ተጠቅማ በቀጠራት ቀን ከሳምንት በኋላ በሰዓቱ ሄደች።እንደደረሰች በሞቀ ፈገግታና ጠበቅ ባለ ሠላምታ ተቀበላትና።
"ቁርስ በልተሻል?›› ሲል ጠየቃት፤ግራገባት፡፡ አሰበች ቁርስ አልበላችም
..ጭርሱኑም ትዝ አላላት።ሳትመልስለት የለበሰውን ነጭ ጋዎን አውልቆ መስቀያው ላይ እያንጠለጠለ
"ጥሩ እኔም አልበላሁም...ወጣ ብለን እንብላ"አላትና ወደ መውጫው መራመድ ሲጀምር ቀድማው ከክፍሉ ወጣች፡፡ቆለፈውና ጎን ለጎን እየተራመዱ መኪናውን ወዳቆመበት ቦታ እየመራ ወሰዳት ፡፡ጋቢናውን ከፈተና ካስገባት በኋላ እሱ ዞሮ ገባና አንቀሳቀሰው… ሆስፒታሉን ለቀው ወጡና አስር ደቂቃ ያህል ከተጓዙ በኋላ የመናፈሻ ድባብ ያለው አሪፍ ሆቴል ይዟት ገባ።ቁርስ እዛው በሉ…ማኪያቶ እየጠጡ ወሬ ጀመሩ።
"ሳምንቱ ጥሩ አለፈ አይደል?"
"ምንም አይል?"
"እንዴት ምንም አይል... አመመሽ እንዴ ...ደውይልኝ ብዬሽ ነበር?››
"አይ ያን ያህል አላመመኝም..ግን ያው ወጣ ገባ ነበር"
"ያው እንዲህ አይነት ህመም በፍጥነት የሚወገድ አይደለም.. የረጅም ጊዜ ክትትልና ትዕግስት ይጠይቃል።በተለይ ያንቺ ጥረት ወሳኝነት አለው፡፡
ምክንያቱም ከበሽታው እንድታገግሚ ለማድረግ የሚያግዙሽ ነገሮች ምን ምን እደሆኑ በዝርዝር ብታውቂያቸውም በሽታው ግን በራሱ ከአንቺ በተቃርኖ ስለሚቆም ተግባራዊ ማድረጉ ፈተና ነው››
‹‹አልገባኝም››
‹‹በቀላሉ ላስረዳሽ… ለምሳሌ ጨጓራ በሽታ ያለበት ሰውን መድሀኒት ትሰጪውና ከዚህና ከዚያ አይነት ምግቦች ተጠበቅ ብለሽ ምክር ብትሰጪው ትዛዙን ለመተግበር የምግብ አምሮቱን መገደብ ብቻ ነው የሚጠበቅበት፤ ስለዚህ በቀላሉ ይከውነዋል፡፡ እንደአንቺ አይነት ችግር ያለበት ሰው ግን ለምሳሌ ጠዋት እንደተነሳሸ አልጋሽን አንጥፊ ብትባይ እሺ አነጥፋለሁ ልትይኝ ትችያለሽ፡፡ግን በተጫጫነሽ ቀን እንኳን ተነስቶ አልጋ ማንጠፍ ይቅርና ..አንሶላውንም ከፊትሽ ላይ ማንሳት ላትችይ ትችያለሽ. .ምክንያቱም ነገሮችን እንድትከውኚ የሚያዘው አእምሮሽ ነው…ችግር የተፈጠረው ዋና ማዘዣ ጣቢያው ላይ በመሆኑ ነገሮች ሁሉ ቀላል አይሆኑም ፡፡እርግጥ በጣም ጥሩ ነገር አሁን ባለው ሁኔታ አንቺ አስቸጋሪው ደረጃ ላይ አልደረስሽም…እንደምንም ተረባርበን ወደኋላ መመለስና ሁሉን ነገር ማስተካከል አለብን፣አሁን ካለሽበት አንድ ስቴፕ ወደፊት ከሄደ ግን ከባድ ነው የሚሆንብን….ለዚህ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርገሽ በከፍተኛ ትእግስት ጤናሽ ላይ ብቻ ማተኮር እንዳለብሽ ከማስጠንቂያ ጋር የምነግርሽ፡፡
"እኔ ደግሞ ትዕግስት ነው የሌለኝ....በቃ ምን ለማግኘት ነው ይሄንን ሁሉ ስቃይ ታግሼ ለመኖር የምጥረው? የሚለው መልስ ያላገኘሁለት ጥያቄ ነው።›
‹‹ግድ የለም፤ መጀመሪያ ካለሽበት የተጨናነቀ ህይወት ራስሽን አላቂና ዘና ባለ መንፈስ ከዛ በኋላ የምትፈልጊውን ሞት ትሞቺያለሽ››
‹‹አይ ዶክተር እየቀለድክብኝ ነው አይደል?››
‹‹አይ እየቀለድኩ አይደለም..ለመሆኑ ስራ እረፍት ላይ ነሽ አይደል?"
"አዎ እረፍት ወስጄያለሁ ..››
‹‹...ምን ያህል?"
‹‹አንድ ወር...ግን ከዛም በኋላ የምመለስ አይመስለኝም ።››
‹‹ሳባ ...ኑሮ አያሳስብሽም አይደል..?.ማለቴ ፋይናንሺያል?"
"ለመጪው መቶ አመት በዚህ ምድር ላይ ብንኖር ገንዘብ የሚቸግረኝ አይመስለኝም።››
"ጥሩ አሁን ወደሆስፒታል እንመለስና በቀደም ካቆምንበት እንቀጥል፤›› አላትና ተያይዘው ወደሆስፒታል ሄዱ።ለአንድ ሰዓት ያህል ካወሩ በኋላ ተጨማሪ አንድ ኪኒን አዘዘላትና ሳምንት በተመሳሳይ ቀን እንዲገናኙ ቀጠሮ በመስጠት አሰናበታት።ስትመጣ ከነበረችበት የበለጠ ተደብራ ነበር የተመለሠችው።ይሄ ሳምንት እየጠበቁ እሱ ጋር መመላለስ ብዙም ምቾት እየሠጣት አይደለም። መኪናዋን እየነዳች ወደቤቷ እየተጓዘች ሳለ ስልኳ ጠራ ...አሁን የያዘችውን ቁጥር በጣም ጥቂት የራሴ የምትላቸው ሰዎች ናቸው የሚያውቁት።ከነዛ ውስጥ ማን እንደደወለላት ለማወቅ በመጓጓት በአንድ እጇ መሪውን እንደያዘች በሌላ እጇ ወደኪሷ ገባችና ስልኩን አወጣች የደዋዩን ማንነት ስታይ ደነገጠች
...መኪናውን ወደዳር አቆመችና አነሳችው ።
"ሄሎ ራጂ"የ12 አመትና የ5ተኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ብቸኛና ተወዳጅ ታናሽ ወንድሟ ነው የደወለላት።እሱን እንኳን ደውላ ካናገረችው አንድ ወር ሊሞላት ነው።‹‹ጨርቄን ጥዬ አልሄድኩም እንጂ እኔማ በትክክል አብጄያለሁ›› ስትል በውስጧ አሰበች።ከእዛኛው ጫፍ ወንድሟ እያወራ ነው።
‹‹እህቴ. ምነው ጠፋሽብን...?ብዙ ጊዜ ስንደውል ስልክሽ አይሰራም››ቅሬታውን አሰማ፡፡
‹‹የእኔ ማር ደህና ነኝ..ትንሽ ስራ ስላጨናነቀኝ ነው..ለመሆኑ እናትህ ደህና ነች››
ከራጂ ጋር በአባት እንጂ በእናት አይገናኙም።ግን የራጅ እናት ለሳባ የእንጀራ እናቷ ብቻ ሳትሆን የልጅነት አብሮ አደግ ጓደኛዋ ጭምር ስለሆነች ቀረቤታቸው ዘመናት ያስቆጠረና የተለየ አይነት ነው።
‹‹እማዬማ...ደህና ነች ማለት ይከብዳል?››
ሳባ ደነገጠች"እንዴ ምን ሆነች...? አመማት እንዴ?››
‹‹እኔ እንጃ እህቴ?.ካንቺ ጋር ተጣልታቹሀል እንዴ?››
‹‹ማንና ማን.. እኔና ስንድ? የት ተገናኝተን...ይሄን ወሬ ከየት አመጣኸው?››
‹‹እህቴ ባትቀየመኝ ኖሮ እንዲህ አትረሳኝም ነበር...አንድ ልጄን አስቀይሜ የአባቷ መንፈስስ እንዴት ይታዘበኛል? እያለች ቀኑን ሙሉ ስታለቅስ ነው የምትውለው.. አይኗ እንዳይጠፋ ፈርቼ ነው የደወልኩልሽ››
ሳባ ጭንቅላቷ ላይ ብው ብሎ የሚነድ እሳት የተነሰነሰባት መሰላት‹‹የእኔ ማር...እናትህ ተሳስታለች...እሷ መቼም እኔን ልታስቀይመኝ አትችልም... ደግሞም በሆነ ነገር ብቀየምስ በግልፅ እንዲህ አድርገሽኛል እላለሁ እንጂ እንዴት እቀየማለሁ፤ ከአንተና ከእሷ ውጭ ሌላ ቤተሠብ አለኝ እንዴ?››
‹‹እሱማ የለሽም...ግን?››
‹‹ግን ምን?››
‹‹እኔ እንጃ ባትቀየሚ.ዛሬ እኛ ጋ ትመጪ ነበራ...››
‹‹የት አሰላ?››
‹‹አዎ ››
ብዥ አለባት ...መድሀኒት ስትወስድ የሚሰማትን የመደንዘዝ አይነት ስሜት ይሰማት ጀመረ..፡፡
‹‹ዛሬ ለምን?››
‹‹ነገ የአባዬ የሰባት አመት መታሰቢያው አይደለ እንዴ....?ባትቀየመኝ በአባቷ መታሰቢያ ቀን ከቤቷ አትቀርም ነበር ብላ እኮ ነው የምታለቅሰው..››
‹‹ራጂ ቆንጆ...አሁን መኪና እየነዳሁ መጥፎ ቦታ ነኝ ያለሁት...ማታ ልደውልልህ››
‹‹እሺ እህቴ እወድሻለሁ፡፡››
‹‹እኔም እወድሀለሁ የእኔ ማር፡፡››ስልኩን ዘጋችና ..መኪናዋን አንቀሳቀሰች ...ወደአስፓልት መሀል ካስገባች በኃላ መጠምዘዣ እስክታገኝ ወደፊት ነዳች፡፡ ከዛ አቅጣጫዋን ለውጣ መንዳት ጀመረች.፡፡
💫ይቀጥላል💫
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፔሩ/አማዞን ወንዝ ላይ
ደግላስ እና ኑሀሚ እታች ወርደው ካፌ ቁጭ ብለው ያዘዙት ቁርስ እስኪመጠ ያነሳቸውን ፎቶና ቪዲዬ ትናንት ከተማውን እየዞሩ ሲጎበኙ የተነሱትንም ጭምር በኢሜሉ ላከችለት፡፡ሁለት ሰዓት ሲሆን ቁርሳቸውን በልተው ጨርሰው ወደ ኤርፖርት ለመሄድ ዝግጁ ሆነው ነበር፡፡እርግጥ ኤርፖርቱ ካረፉበት ሆቴል 15 ደቂቃ ያህል ብቻ ነው የሚርቀው፡፡ቢሆንም ቀድመው ሄደው እዛው ለመጠበቅ ተስማሙና ለሆቴሉ አስተናጋጅ ታክሲ እንዲጠራላቸው ነገሩት፡፡በአምስት ደቂቃ ውስጥ የፈለጉት ታክሲ መጣና ጫናቸው፡፡ሁለቱም ከኋላ ወንበር ተጠጋግተው ተቀምጠው በፀጥታ ጉዞቸውን ጀመሩ፡፡ሹፌሩ ታክሲ ከሚነዳ ይልቅ ቱርቦ ወይም ግዙፍ ተሳቢ መኪና ቢነዳ ከአቋሙ ጋር ይሄድ ነበር…እጆቹና አንገቱ ጠቅላላ በንቅሳት የተዝጎረጎረ.. ግዙፍ ግን ባለ አስፈሪ ጡንቻ ባለቤት የሆነ ሰው ነው፡፡የከተማውን ግራና ቀኝ ፎቆች እና የንግድ ተቋሞችን እየተመለከቱ ለ15 ደቂቃ ከተጓዙ በኃላ ሹፌሩ ወደኃላ በመዞር…‹‹ካላስቸገርኳችሁ እዚህ ፊት ለፊታችን ካለው ቅያስ ጋር የምቀበለው እቃ ነበረኝ..ሁለት ደቂቃ ባዘገያችሁ ነው››ሲል በተሰባበረ እንግሊዘኛ ፍቃድ ጠየቃቸው፡፡
ቢያንስ ከ30 ደቂቃ በላይ ትርፍ ሰዓት ስላላቸው እና ከዛ ላይ አንድ 5 ደቂቃ ቢለግሱት የሚጎዳቸው መስሎ ስላልተሰማቸው አልተቃወሙትም፡፡
‹‹..ችግር የለም.. እንችላለን፡፡››ስትል ሁለቱንም ወክላ ፍቃዱን የሰጠችው ኑሀሚ ነች፡፡ እንዳለውም በመጀመሪያው ቅያስ ወደግራ ታጠፈና ጠባብ የድንጋይ ንጣፍ የሆነ መንገድ ውስጥ ገባ፡፡ጭር ያለ መንገድ ነው፡፡ሁለት መቶ ሜትር ያህል ከተጓዘ በኃላ ጥግ አሲይዞ መኪናውን አቋመና ፡፡‹‹መጣሁ ሁለት ደቂቃ›› በማለት ሞተሩን ሳያጠፋ ታክሲዋን ለቀቀና ወጥቶ አንድ የብረት በር ግቢ ገፋ አድርጎ ገባ ፡፡ሁለቱም አይናቸውን እሱ የገባበት ግቢ ላይ ተክለው ከአሁን አሁን ወጣ እያሉ ሲጠብቁ በቅፅበት ከግራና ከቀኝ ያለው በራፍ ተከፈተና ጭንብል ያጠለቁና ሽጉጥ የደቀኑ ሰዎች የመኪናውን በራፍ ከፍተው ገቡና ሁለቱን አንድ ላይ አጣብቀው ከመሀላቸው በመክተት በሽንጣቸው አቅጣጫ ሽጉጣቸውን ደቀኑባቸው፡፡ ኑሀሚም ሆነች ዳግላስ በድንጋጤ ትንፋሽ አጠራቸው፡፡ ልክ ቀድመው እንደገቡት ጭንብል ያጠለቀ ሌላ ሰው ከፊት ለፊት የሹፌሩን ቦታ ያዘና መኪናውን አንቀሳቀሳት፡፡ቀጥታ ወደፊት ለፊቱ ነው እየነዳ ያለው፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ ሙሉ በሙሉ ከከተማ ወጡና ረግረግ የሆነና ግራና ቀኙ በደን በተሸፈነ ከዛም አልፎ በጭቃ የላቆጠ ወጣ ገባ መንገድ ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹ምንድነው የምትፈልጉት….?ገንዘብ ነው…?››ኑሀሚ ነች ጠያቂው፡፡
አንደኛው መናገር ጀመረ፡፡ኑሀሚ ግን ምንም እየገባት አይደለም፡፡ቋንቋው እስፓኒሽ ነው፡፡እሷ ደግሞ ከእንግሊዘኛ ውጭ ሌላ የውጭ ቋንቋ አታውቅም፡፡ እርግጥ ራሺኛ ትችላለች..ያ ግን እዚህ አካባቢ እርባን ያለው መስሎ አልተሰማትም፡፡አጠገቧ ወዳለው ዳግላስ ዞረችና አፍጥጣ አየችው‹‹አፍሽን ዝጊ ነው የሚሉት፡፡››ሲል ተረጓመላት፡፡
‹‹ቋንቋውን ትችላለህ እንዴ?››
‹‹የሚሉትን መስማት የቻልኩት ብችል ነዋ››ሲል መለሰላት፡፡
አስር ደቂቃ በኋላ ጫካና ቁጥቆጦ እያቆራረጡ ከተጓዙ በኃላ መኪናዋ ቆመች፡፡ግራና ቀኛቸው ተቀምጠው ሽጉጥ የደቀኑባቸው ሰዎች አንዳንዳቸውን ይዘው ከታክሲዋ ወረዱ፡፡ሹፌሩም የታክሲዋን ሞተር አጥፍቶ ወረደ ፡፡
መኪናዋን ሲሾፍር የነበረው..ከጃኬቱ ኪስ ውስጥ እነሱ የለበሱትን አይነት ጥቁር የፊት ጭንብል አወጣና ተራ በተራ አጠለቀባቸው፡፡፡ከዛ ሌላ ጥቁር ጨርቅ አወጣና በአይናቸው ዙሪያ በማሽከርከር አሰረና ሙሉ በሙሉ እንዳያዩ አደረጋቸው፡፡ከዛ እየጎተቱና እያመናጨቁ በእግር ይዘዋቸው መጓዝ ጀመሩ፡፡ኑሀሚ በጣም ተረበሸች፡፡በቀልቃላነቷም እራሷን በጣም ወቀሰች፡፡‹‹እንዴት ሰው በማያውቀው ሀገር የማያውቀውን ሰው ለመርዳት ይሄን ሁሉ ርቀት ይጓዛል ?ለዛውም ምን እንደሆነ እና ማን መሆኑን ለማያውቅ ሰው?ከእኔ እንደዚህ አይነት ስህተት ፈፅሞ አይጠበቅም፡፡››ስትል አሰበች፡፡
.እርግጥ ኑሀሚ በህይወቷ ከህፃንነቷ ጀምሮ ብዙ ይሄንን መሰል አደጋዎችና አሳልፋለች፡፡ሞትኩ በቃ አበቃልኝ ካለች በኋላ ባልተጠበቀ ቅፅበታዊ ገጠመኝ ከመከራውም ወጥታ ህይወቷንም ያተረፈችበት አጋጣሚ በርካታ ናቸው፡፡ግን ያን ሁሉ ፈተና ያን ሁሉ ተስፋ መቁረጥ አጋጥሟት የነበረው በገዛ ሀገሯ በገዛ ህዝቦቾ ውስጥ ነው፡፡በሀገር ውስጥ በገዛ ምድር ላይ እየተራመዱ ተስፋ መቁረጥ በሰው ሀገር ውስጥ የሰው ምድር ላይ እየተራመዱ ተስፋ ከመቁረጥ ፍፁም የተለየ ነው፡፡በገዛ ሀገር ሆኖ ተስፋ መቁረጥ ማለት ሁል ጊዜ የተደበቀች ተስፋ ትኖራለች፡፡ያቺ ተስፋ ከእናት የምትገኝ ወይ ከአባት የምትቸር ወይም ወንድም የሚለኩሳት..ወይ ደግሞ እህት የምታበራት የአይዞህ ባይነት ተስፋና አለውልህ የሚል ማፅናኛ ነች፡፡ያ ቃል ደግሞ የተገነዘ ተስፋን ከሞት የሚያስነሳ ይሆናል፡፡በሰው ሀገር ተስፋ ሲቆረጥ ግን እነዚህ ሁሉ የሉም፡፡
እየተደናበሩና እየተገፋፉ 15 ደቂቃ ከተጓዙ በኃላ ተረጋጉ፡፡ከአይናቸው ላይ የታሰረው ጥቁር ጨርቅም ሆነ ጭንብል ተነሳላቸው፡፡ከጀርባቸው ጥቅጥቅ ጫካ …ከፊት ለፊታቸው የተንጣለለ የአማዞን ወንዝ ነው የሚታየው፡፡እነሱ ከቆሙበት በሁለት ሜትር ርቀት መለስተኛ የሞተር ጀልባ መልህቋን ጥላ ቆማለች፡፡አንዱ እጇን ያዛትና እየጎተተ ወሰዳት እና አንደኛው ጀልባ ላይ ጫናት…ልክ እንደእሷ ሁሉ ዳግላስንም አምጥተው ከጎኔ ያስቀምጡታል ብላ ስትጠብቅ..በተቃራኒው ወሰዱና ሌለኛው ጀልባ ላይ ጫኑት፡፡
‹‹ለምንድነው የምትለያዩን..?ወዴት ነው የምትወስዱን ..?እኔ እኮ ምንም አላውቅም፡፡ከእሱ ጋር የተገናኘሁት ትናንትና ነው፡፡ምንም ማውቀው ነገር የለኝም…?››ኑሀሚ ለፈለፈች፡፡ቁብ ሰጥቶ እያዳመጣት ያለ ሰው የለም፡፡እሷ ራሱ ያንን ሁሉ ስትለፈለፍ የነበረው በአማርኛ ነበርና ያ ትዝ ሲላት የምሬት ፈገግታ ፈገግ አለች፡፡ሁለት ሽጉጥ የደቀኑ አጋቾች በአንድ ሜትር ከእሷ ፈንጠር ብለው ሁለት ሌላ መሳሪያ የታጠቁ ደግሞ ከጀርባዋ ተቀመጡ፡፡ጀልባዋ አስደንጋጭ የሞተር ጩሀት ድምፅ አሰማችና ወደባህሩ መሀከል ተፈተለከች፡፡…ወንድሟ ትዝ አላት…፡፡እህቴ ከዛሬ ነገ ትመጣለች እያለ ሲጠብቅ…..መኖር መሞቷን እንኳን ማረጋገጥ ሳይችል በስቃይ ሲኖር አሰበችና ስቅጥጥ አላት ..አይኖቾን አሻግራ ላከችና ዳግላስ የተጫነበትን ጀልባ ለማየት ሞከረች፡፡እነሱ እየተጓዙ ካሉበት አቅጣጫ በተቃራኒው ነው ይዘውት እየሄዱ ያሉት፡፡በቃ መቼም እንደማይገናኙ አሰበች…..እሷ እራሷ አሳዛኝ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ለእሱ ከማዘን እራሷን ማቀብ አልቻለችም፡፡
ፔሩና/ኮሎምቢ ድንበር
በአለም ላይ በውሀ ከተከበብት ከተሞች መካከል ግዙፍ የሆነችውንና እስከ 200 ሺ ህዝብ በላይ ከሚኖርባትን የኢኩኢቶስ ከተማ ነጥቀው በአማዞን ወንዝ ላይ እያንሳፈፉ አርቀው ወሰዷትና አማዞን ደን ውስጥ ከተቷት።ከጀልባው ወርዳ መሬት ላይ ስታርፍ ይዛዋት የመጡት አራት ሰዎች በመጡበት ጀልባ ወደኃላ ሲመለሱ …መሬት ላይ ቆመው ሲጠብቋት የነበሩ ከነዛኞቹ በላይ አስፈሪ የሆኑ በቁጥር 9 አካባቢ ሰዎች ነበሩ የተቀበሏት፡፡‹‹በዚህ ሁሉ ትጥቅና አጀብ የሚቀበሉኝ ማነች ብለው ነገሯቸው ይሆን?›› ስትል በውስጧ አልጎመጎች፡፡አራቱ ከኃላዋ አራቱ ደግሞ ከፊት አንዱ ከመሀከላቸው በአቋሙ ቀጠን የሚል በአለባበሱ ስርአት ያለውና ..ለስላሳ ቢጤ የሆነ ሰው ወደእሷ ቀረበና
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፔሩ/አማዞን ወንዝ ላይ
ደግላስ እና ኑሀሚ እታች ወርደው ካፌ ቁጭ ብለው ያዘዙት ቁርስ እስኪመጠ ያነሳቸውን ፎቶና ቪዲዬ ትናንት ከተማውን እየዞሩ ሲጎበኙ የተነሱትንም ጭምር በኢሜሉ ላከችለት፡፡ሁለት ሰዓት ሲሆን ቁርሳቸውን በልተው ጨርሰው ወደ ኤርፖርት ለመሄድ ዝግጁ ሆነው ነበር፡፡እርግጥ ኤርፖርቱ ካረፉበት ሆቴል 15 ደቂቃ ያህል ብቻ ነው የሚርቀው፡፡ቢሆንም ቀድመው ሄደው እዛው ለመጠበቅ ተስማሙና ለሆቴሉ አስተናጋጅ ታክሲ እንዲጠራላቸው ነገሩት፡፡በአምስት ደቂቃ ውስጥ የፈለጉት ታክሲ መጣና ጫናቸው፡፡ሁለቱም ከኋላ ወንበር ተጠጋግተው ተቀምጠው በፀጥታ ጉዞቸውን ጀመሩ፡፡ሹፌሩ ታክሲ ከሚነዳ ይልቅ ቱርቦ ወይም ግዙፍ ተሳቢ መኪና ቢነዳ ከአቋሙ ጋር ይሄድ ነበር…እጆቹና አንገቱ ጠቅላላ በንቅሳት የተዝጎረጎረ.. ግዙፍ ግን ባለ አስፈሪ ጡንቻ ባለቤት የሆነ ሰው ነው፡፡የከተማውን ግራና ቀኝ ፎቆች እና የንግድ ተቋሞችን እየተመለከቱ ለ15 ደቂቃ ከተጓዙ በኃላ ሹፌሩ ወደኃላ በመዞር…‹‹ካላስቸገርኳችሁ እዚህ ፊት ለፊታችን ካለው ቅያስ ጋር የምቀበለው እቃ ነበረኝ..ሁለት ደቂቃ ባዘገያችሁ ነው››ሲል በተሰባበረ እንግሊዘኛ ፍቃድ ጠየቃቸው፡፡
ቢያንስ ከ30 ደቂቃ በላይ ትርፍ ሰዓት ስላላቸው እና ከዛ ላይ አንድ 5 ደቂቃ ቢለግሱት የሚጎዳቸው መስሎ ስላልተሰማቸው አልተቃወሙትም፡፡
‹‹..ችግር የለም.. እንችላለን፡፡››ስትል ሁለቱንም ወክላ ፍቃዱን የሰጠችው ኑሀሚ ነች፡፡ እንዳለውም በመጀመሪያው ቅያስ ወደግራ ታጠፈና ጠባብ የድንጋይ ንጣፍ የሆነ መንገድ ውስጥ ገባ፡፡ጭር ያለ መንገድ ነው፡፡ሁለት መቶ ሜትር ያህል ከተጓዘ በኃላ ጥግ አሲይዞ መኪናውን አቋመና ፡፡‹‹መጣሁ ሁለት ደቂቃ›› በማለት ሞተሩን ሳያጠፋ ታክሲዋን ለቀቀና ወጥቶ አንድ የብረት በር ግቢ ገፋ አድርጎ ገባ ፡፡ሁለቱም አይናቸውን እሱ የገባበት ግቢ ላይ ተክለው ከአሁን አሁን ወጣ እያሉ ሲጠብቁ በቅፅበት ከግራና ከቀኝ ያለው በራፍ ተከፈተና ጭንብል ያጠለቁና ሽጉጥ የደቀኑ ሰዎች የመኪናውን በራፍ ከፍተው ገቡና ሁለቱን አንድ ላይ አጣብቀው ከመሀላቸው በመክተት በሽንጣቸው አቅጣጫ ሽጉጣቸውን ደቀኑባቸው፡፡ ኑሀሚም ሆነች ዳግላስ በድንጋጤ ትንፋሽ አጠራቸው፡፡ ልክ ቀድመው እንደገቡት ጭንብል ያጠለቀ ሌላ ሰው ከፊት ለፊት የሹፌሩን ቦታ ያዘና መኪናውን አንቀሳቀሳት፡፡ቀጥታ ወደፊት ለፊቱ ነው እየነዳ ያለው፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ ሙሉ በሙሉ ከከተማ ወጡና ረግረግ የሆነና ግራና ቀኙ በደን በተሸፈነ ከዛም አልፎ በጭቃ የላቆጠ ወጣ ገባ መንገድ ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹ምንድነው የምትፈልጉት….?ገንዘብ ነው…?››ኑሀሚ ነች ጠያቂው፡፡
አንደኛው መናገር ጀመረ፡፡ኑሀሚ ግን ምንም እየገባት አይደለም፡፡ቋንቋው እስፓኒሽ ነው፡፡እሷ ደግሞ ከእንግሊዘኛ ውጭ ሌላ የውጭ ቋንቋ አታውቅም፡፡ እርግጥ ራሺኛ ትችላለች..ያ ግን እዚህ አካባቢ እርባን ያለው መስሎ አልተሰማትም፡፡አጠገቧ ወዳለው ዳግላስ ዞረችና አፍጥጣ አየችው‹‹አፍሽን ዝጊ ነው የሚሉት፡፡››ሲል ተረጓመላት፡፡
‹‹ቋንቋውን ትችላለህ እንዴ?››
‹‹የሚሉትን መስማት የቻልኩት ብችል ነዋ››ሲል መለሰላት፡፡
አስር ደቂቃ በኋላ ጫካና ቁጥቆጦ እያቆራረጡ ከተጓዙ በኃላ መኪናዋ ቆመች፡፡ግራና ቀኛቸው ተቀምጠው ሽጉጥ የደቀኑባቸው ሰዎች አንዳንዳቸውን ይዘው ከታክሲዋ ወረዱ፡፡ሹፌሩም የታክሲዋን ሞተር አጥፍቶ ወረደ ፡፡
መኪናዋን ሲሾፍር የነበረው..ከጃኬቱ ኪስ ውስጥ እነሱ የለበሱትን አይነት ጥቁር የፊት ጭንብል አወጣና ተራ በተራ አጠለቀባቸው፡፡፡ከዛ ሌላ ጥቁር ጨርቅ አወጣና በአይናቸው ዙሪያ በማሽከርከር አሰረና ሙሉ በሙሉ እንዳያዩ አደረጋቸው፡፡ከዛ እየጎተቱና እያመናጨቁ በእግር ይዘዋቸው መጓዝ ጀመሩ፡፡ኑሀሚ በጣም ተረበሸች፡፡በቀልቃላነቷም እራሷን በጣም ወቀሰች፡፡‹‹እንዴት ሰው በማያውቀው ሀገር የማያውቀውን ሰው ለመርዳት ይሄን ሁሉ ርቀት ይጓዛል ?ለዛውም ምን እንደሆነ እና ማን መሆኑን ለማያውቅ ሰው?ከእኔ እንደዚህ አይነት ስህተት ፈፅሞ አይጠበቅም፡፡››ስትል አሰበች፡፡
.እርግጥ ኑሀሚ በህይወቷ ከህፃንነቷ ጀምሮ ብዙ ይሄንን መሰል አደጋዎችና አሳልፋለች፡፡ሞትኩ በቃ አበቃልኝ ካለች በኋላ ባልተጠበቀ ቅፅበታዊ ገጠመኝ ከመከራውም ወጥታ ህይወቷንም ያተረፈችበት አጋጣሚ በርካታ ናቸው፡፡ግን ያን ሁሉ ፈተና ያን ሁሉ ተስፋ መቁረጥ አጋጥሟት የነበረው በገዛ ሀገሯ በገዛ ህዝቦቾ ውስጥ ነው፡፡በሀገር ውስጥ በገዛ ምድር ላይ እየተራመዱ ተስፋ መቁረጥ በሰው ሀገር ውስጥ የሰው ምድር ላይ እየተራመዱ ተስፋ ከመቁረጥ ፍፁም የተለየ ነው፡፡በገዛ ሀገር ሆኖ ተስፋ መቁረጥ ማለት ሁል ጊዜ የተደበቀች ተስፋ ትኖራለች፡፡ያቺ ተስፋ ከእናት የምትገኝ ወይ ከአባት የምትቸር ወይም ወንድም የሚለኩሳት..ወይ ደግሞ እህት የምታበራት የአይዞህ ባይነት ተስፋና አለውልህ የሚል ማፅናኛ ነች፡፡ያ ቃል ደግሞ የተገነዘ ተስፋን ከሞት የሚያስነሳ ይሆናል፡፡በሰው ሀገር ተስፋ ሲቆረጥ ግን እነዚህ ሁሉ የሉም፡፡
እየተደናበሩና እየተገፋፉ 15 ደቂቃ ከተጓዙ በኃላ ተረጋጉ፡፡ከአይናቸው ላይ የታሰረው ጥቁር ጨርቅም ሆነ ጭንብል ተነሳላቸው፡፡ከጀርባቸው ጥቅጥቅ ጫካ …ከፊት ለፊታቸው የተንጣለለ የአማዞን ወንዝ ነው የሚታየው፡፡እነሱ ከቆሙበት በሁለት ሜትር ርቀት መለስተኛ የሞተር ጀልባ መልህቋን ጥላ ቆማለች፡፡አንዱ እጇን ያዛትና እየጎተተ ወሰዳት እና አንደኛው ጀልባ ላይ ጫናት…ልክ እንደእሷ ሁሉ ዳግላስንም አምጥተው ከጎኔ ያስቀምጡታል ብላ ስትጠብቅ..በተቃራኒው ወሰዱና ሌለኛው ጀልባ ላይ ጫኑት፡፡
‹‹ለምንድነው የምትለያዩን..?ወዴት ነው የምትወስዱን ..?እኔ እኮ ምንም አላውቅም፡፡ከእሱ ጋር የተገናኘሁት ትናንትና ነው፡፡ምንም ማውቀው ነገር የለኝም…?››ኑሀሚ ለፈለፈች፡፡ቁብ ሰጥቶ እያዳመጣት ያለ ሰው የለም፡፡እሷ ራሱ ያንን ሁሉ ስትለፈለፍ የነበረው በአማርኛ ነበርና ያ ትዝ ሲላት የምሬት ፈገግታ ፈገግ አለች፡፡ሁለት ሽጉጥ የደቀኑ አጋቾች በአንድ ሜትር ከእሷ ፈንጠር ብለው ሁለት ሌላ መሳሪያ የታጠቁ ደግሞ ከጀርባዋ ተቀመጡ፡፡ጀልባዋ አስደንጋጭ የሞተር ጩሀት ድምፅ አሰማችና ወደባህሩ መሀከል ተፈተለከች፡፡…ወንድሟ ትዝ አላት…፡፡እህቴ ከዛሬ ነገ ትመጣለች እያለ ሲጠብቅ…..መኖር መሞቷን እንኳን ማረጋገጥ ሳይችል በስቃይ ሲኖር አሰበችና ስቅጥጥ አላት ..አይኖቾን አሻግራ ላከችና ዳግላስ የተጫነበትን ጀልባ ለማየት ሞከረች፡፡እነሱ እየተጓዙ ካሉበት አቅጣጫ በተቃራኒው ነው ይዘውት እየሄዱ ያሉት፡፡በቃ መቼም እንደማይገናኙ አሰበች…..እሷ እራሷ አሳዛኝ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ለእሱ ከማዘን እራሷን ማቀብ አልቻለችም፡፡
ፔሩና/ኮሎምቢ ድንበር
በአለም ላይ በውሀ ከተከበብት ከተሞች መካከል ግዙፍ የሆነችውንና እስከ 200 ሺ ህዝብ በላይ ከሚኖርባትን የኢኩኢቶስ ከተማ ነጥቀው በአማዞን ወንዝ ላይ እያንሳፈፉ አርቀው ወሰዷትና አማዞን ደን ውስጥ ከተቷት።ከጀልባው ወርዳ መሬት ላይ ስታርፍ ይዛዋት የመጡት አራት ሰዎች በመጡበት ጀልባ ወደኃላ ሲመለሱ …መሬት ላይ ቆመው ሲጠብቋት የነበሩ ከነዛኞቹ በላይ አስፈሪ የሆኑ በቁጥር 9 አካባቢ ሰዎች ነበሩ የተቀበሏት፡፡‹‹በዚህ ሁሉ ትጥቅና አጀብ የሚቀበሉኝ ማነች ብለው ነገሯቸው ይሆን?›› ስትል በውስጧ አልጎመጎች፡፡አራቱ ከኃላዋ አራቱ ደግሞ ከፊት አንዱ ከመሀከላቸው በአቋሙ ቀጠን የሚል በአለባበሱ ስርአት ያለውና ..ለስላሳ ቢጤ የሆነ ሰው ወደእሷ ቀረበና
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ከጥዋቱ ሁለት ሰዓት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀኝ እጇ የመሀል ጣት ተነቃነቀ…እቤቱ ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ በደስታ ፈገገ ..ከአስር ደቂቃ በኋላ አይኖቾ ተከፈቱ፣አራቱም የቤቱ አባላት የተኛችበትን ፍራሽ በሁሉም አቅጣጫ ከበው በፈገግታ ያዩት ጀመር….ግራ ገባት፡፡መልሳ አይኖቾን ጨፈነች…፡፡መንቃቷ እራሱ የእውነት ሳይሆን በህልም አለም ውስጥ የተፈጠረ መንቃት ነው የመሰላት ፡፡ለዛ ነው ዳግመኛ እይኖቾን የጨፈነችው..፡፡መልሳ ስትገልጥ ያየችው ተመሳሳይ ነገር ነው….አራት ወዛቸው የተመጠጠ የለበሱት ልብስ የነታተበ ..በአባቷ ግቢ ውስጥ አትክልቶችን ከሚንከባከቡ ሰራተኞች በላይ ኑሮ የጠበሳቸው ጠና ያሉ ሰውዬ…ቆዳቸው የተሸበሸበ እናት… የ ሀያ አመት ልጅ እግር የምታምር ግን ደግሞ ያልተመቻት ልጃገረዶች..ባለጡንቻ ፈርጣማ እና ባለኮስታራ ፊት ሀያ አምስት ወይም ስድስት የሚሆነው ወጣት ..ጭስ የጠጣና ያረጀ የማዳበሩያ ኮርኒስ ያለው ጠባብ ክፍል…መሬት ላይ የተነጠፈ ፍራሽና ያረጀ በህይወቷ እንኳን ለብሳው አይታው የማታውቀው አይነት ብርድ ልብስ ለብሳ ነበር እራሷን ያገኘችው፡፡ግን እንደዛም ሆኖ የተለየ እና የማታውቀው ቦታ ያለች መስሎ አልተሰማትም….የሆነ ከዘመናት በፊት ታውቀው የነበረ እና ስትናፍቀው የቆየችው ቦታ ተመልሳ እንደመጣች አይነት ስሜት ነው እየተሰማት ያለው
‹‹…የት ነኝ?››
‹‹ልጄ…አሁን ሰላም ነሽ …ትንሽ አደጋ ደርሶብሽ ነው?››
‹‹የምን አደጋ?››
‹‹አሁን ሰላም ነሽ..በውድቅት ለሊት ሞተር ስትነጂ ነበር…ተገልብጠሸ ነው፡፡››
‹‹ሞተር››
‹‹አዎ..ሞተር..ከማን ስትሸሺ ነበር….?እስከአሁን ለፖሊስ አላሳወቅንም…..ይሄውሽ እኔና ቤተሰቦቼ በህይወት ፈተና ጋር ግብግብ ገጥመን በትግል የምንኖር ሰዎች ነን…ከሆነ ወንጀል ጋር የተያያዘ ታሪክ ካለሽ እባክሽ.እኛንም ጣጣ ውስጥ እንዳንገባ ከአሁኑ ንገሪን››ሲል ፊራኦል ተናገረ፡፡
‹‹ምነካህ ልጄ? ልጅቷ ገና አሁን መንቃቷ ነው…ተው እንጂ ነውር ነው›እናትዬው ገሰፁት..አባትዬውም ለባለቤታቸው ድጋፍ በመስጠት‹‹ልጄ አዎ..አሁን ዋናው ያንቺ መትረፍ ነው ፡፡ሌላውን ቀላል ነው…የሰው ልጅ በህይወት ካለ የማያልፈው መከራ የማያሸነፍው የህይወት ትግል የለም..አሁን አንቺ ምንም አታስቢ..እኔነኝ የተባለ ውጌሻ ጠርቼያለሁ፡፡ ወለምታ ወይም ስብራት ነገር ካለሽ ያዩልሻል…ከዛ ካገገምሽ በኋላ ለቤተሰቦችሽ እንደውልላቸውና መጥተው ይወስዱሻል››
በፀሎት ለሊት በውድቅት ለሊት ከቤቷ አምልጣ እንዴት እንደወጣችና ምን እንዳደረገችና አሁን ያለችበት ቤትም የእነማን እንደሆነ ትዝ እያላት ሲመጣ ….የመረጋገትና የደስታ ስሜት ተሰማት
‹‹አመሰግናለሁ…ምንም ወንጀል አልሰራሁም….ፖሊስም እየፈለገኝ አይደለም…አሁን ደክሞኛል ልተኛ..››አለችና መልሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡
‹‹ሰማችሁ አይደል..ምንም ወንጀል አልሰራሁም ብላለች..አሁን ዞር በሉላት …ትንፋሻችሁ እራሱ በሽታ ነው የሚሆናባት››አባትዬው ተቆጡ፡፡
‹‹አባዬ ደግሞ ፣አንተ ሁል ጊዜ ሰው እንዳመንክ ነው.. ሚገርመው ደግሞ ሰዎች ቃላቸውን እያጠፉ አንተን ማሳዘናቸውን አያቆሙም… አንተም ደግሞ ደግመህ ደጋግመህ እነሱን ማመንህን አታቆምም››ፊራኦል ተነጫነጨ፡፡
‹‹ልጄ ገለባ ቢዘሩት አይበቅልም ተጠራጣሪ ሰው አይፀድቅም ይባላል..ያገኘሁትን ሰው ሁሉ በመጠራጠር ህይወቴን ሳሰቃይ ከመኖር እያመንኩ ብከዳ ይሻለኛል…ቢያንስ በማመኔ ምክንያት የሚደርስብኝ ችግር ምክንያቱ እኔ አይደለሁም..››
ፊራኦል በወላጆቹ ውሳኔ ባለመስማማት ‹‹በሉ እሺ እኔ ወደ ስራ ሄጃለሁ፡፡››በማለት ቤተሰቡን ተሰናብቶ ግቢውን ለቆ ሲወጣ በራፍ ላይ ውጌሻዋ ወደውስጥ ስትገባ ተላለፉ፡፡
‹‹ቤቶች አቶ ለሜቻ››ሁሉም ግር ብለው ወጥተው ውጌሻዋን ተቀበሉና ወደውስጥ አስገቧት፡፡
‹‹የትኛው ልጅህ ነች… ለሜቻ?››
‹‹የወንድሜ ልጅ ነች ከድሬደዋ ልትጠይቀኝ መጥታ ነው››
‹‹እና ምን ገጥሟት ነው?››
‹‹ባኮት ከሆነ የሰፈር ልጅ ጋር ሞተር ተፈናጣ ስትሄድ ሞተሩ ተገለበጠባቸውና ትንሽ ተጎዳች..ምን አልባት ስብራት ወይም ወለምታ ይኖራት እንደሆነ ብለን ስለተጠራጠርን ነው ያስቸገርኖት፡፡››
በፀሎት የሚነጋገሩትን ሁሉ አይኖቾን ጨፍና እየሰማች ነው…
‹‹ታዲያ ተኝታለች?››
‹‹አሁን ነቅታ ነበር…እንዴት ነው እንቀስቅሳት?››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠየቁ፡፡
‹‹አይ ቆይ ተዋት ..ህመሙ እራሱ ይቀሰቅሳታል፡፡››አሉና ስሯ ፍራሽ ላይ ተቀመጡ…
‹‹ እስቲ እሱን የከሰል ፍም አቅርቡልኝ››ትዕዛዝ ሰጡ፡፡
ማንደጃው ቀረበላቸው…‹‹ እስኪ አንዳችሁ ኑና የለበሰችውን ልብሷን አውልቁላት…..››ለሊሴ ፈጠን ብላ መጣችና ከላይ የለበሳቸውን ጃኬት… ቦዲ ተራ በተራ አወለቀችላት… በጡት ማስያዣ ብቻ አስቀረቻት ፡፡አንገቷ ላይ ያለው የእጅ መዳፍ የሚያህል አብረቅራቂ እንቁ ፈርጥ ያለበት ጌጥ የሁሉንም አይን በቅፅበት ተቆጣጠረ
….ጆሮዋ ላይም ያንጠለጠለችው የጆሮ ጌጥ ከአንገት ሀብሏ ጋር እንዲናበብ ተደርጎ የተሰራ ለልደት በዓሏ ከአባቷ የተበረከተላት ልዩ አይነት ጌጥ ስለሆን በተለይ የሌሊሳን ትኩረት በደንብ ነው የተቆጣጠረው…ሁሉም ግን አርቴ እንጂ ትክክለኛ ነው ብለው አላሰቡም ነበር፡፡
ውጌሻዋ ቦርሳቸው ውስጥ እጃቸውን ሰደዱና በብልቃጥ ከለጋ ቅቤ ጋር ተለውሶ የተዘጋጀ መዳህኒታቸውን አወጡና ፊት ለፊታቸው አስቀምጠው በሌባ ጣታቸው ዛቅ እያደረጉና በመሀል አጣታቸው ላይ አድርገው በመላ መዳፋቸው ላይ ለቀለቁና ስራቸው በቀረበላቸው የከስል ፍም ላይ ጠጋ አድርገው ሙቀት እንዲያገኝ ካደረጉ በኃላ ከአንገቷ ጀምሮ ትከሻዋን እያሹ መፈተሽ ጀመሩ‹‹ ..ምንም አልሆነችም እስኪ ሱሪዋን አውልቁልኝ››ሌላ ትዕዛዝ ሰጡ..በዚህ ጊዜ አቶ ለሜቻ ከተቀመጡበት ተነሱና ወደውጭ ወጡ..ሴቶቹ እንደምንም
ታጋግዘው የለበሰችውን ጅንስ ሱሪ ከላዮ ላይ አወለቁና በፓንት ብቻ ለውጌሻዋ አስረከቧት
…ውጌሻዋ ተመሳሳዩን እሽት ከጭኖቾ ጀመረው ወደታች መውረድ ጀመሩ…ቀኝ እግሯ ቁርጭምጭሚቷ ጋር ደርሰው ጨበጥ..ጨበጥ ሲያደርጓት ግን ከተኛችበት እንደመብረቅ አጓርታ ተነስታ ቁጭ አለች…ሁሉም በድንጋጤ የሚያደርጉት ጠፋቸው..‹‹አዎ እዚህ ጋር ችግር አለ‹‹አሁን በደንብ አድርጋችሁ ግራና ቀኝ ትከሻዋን ያዟት፡፡››የውጌሻዋን ትዕዛዝ ስትሰማ አይኖቾ በፍራቻ ተጉረጠረጠ፡፡በእድሜዋ መርፌ ለመወጋት እሩሱ በስንት እዝጊዎታና ማባበያ ነው...ታዲያ አሁን እንዲህ ላይቨ በስቃይ ስትፈተን እንባዋ ረገፈ
፡፡እናትና ልጅ ግራና ቀኛ ትከሻዋን አጥብቀው እንዳትነቃነቅ ያዙዋት..ሴትዬዋ እየጨመቁና እያሽከረከሩ ያሾት ጀመር…በህይወቷ ተስምቷት የማያውቀው አይነት ህመም…..ተሰማት..የሆነ መጋዝ ጥርስ ያለው አዞ በሁለት መንጋጋዎች መሀከል እግሮቾን አስገብቶ እያኘካት ነው የመሰላት..እንባዋ ብቻ ሳይሆን ንፍጦም በአፍንጫ ላይ እየተዝረከረከ እንደሆነ ይታወቃታል…ለዛ ግን የምትጨነቅበት ሁኔታ ላይ አይደለችም…..ውጌሻዋ ከ10 ደቂቃ በኃላ የተሰበረውን አጥንት ወደቦታው ከመለሱ በኃላ እንዳይነቃነቅ በቀርከሃ በደንብ አድርገው ካሰሩት በኋላ በፋሻ ጠቅልለው አጠናቀቁ…ከዛ እቃቸውን ሰብስባው ተነሱ…ለሊሴ የራሷን ቢጃማ አለበሰችትና መልሰው አስተኞት፡፡
‹‹እልፍነሽ››
‹‹አቤት እማማ››
‹‹ለሜቻ ድሬደዋ ሀብታም ወንድም አለው እንዴ?››
ወ.ሮ እልፍነሽ ጥያቄው መደናገር ውስጥ አስገባቸው‹‹ለምን ጠየቁኝ?››
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ከጥዋቱ ሁለት ሰዓት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀኝ እጇ የመሀል ጣት ተነቃነቀ…እቤቱ ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ በደስታ ፈገገ ..ከአስር ደቂቃ በኋላ አይኖቾ ተከፈቱ፣አራቱም የቤቱ አባላት የተኛችበትን ፍራሽ በሁሉም አቅጣጫ ከበው በፈገግታ ያዩት ጀመር….ግራ ገባት፡፡መልሳ አይኖቾን ጨፈነች…፡፡መንቃቷ እራሱ የእውነት ሳይሆን በህልም አለም ውስጥ የተፈጠረ መንቃት ነው የመሰላት ፡፡ለዛ ነው ዳግመኛ እይኖቾን የጨፈነችው..፡፡መልሳ ስትገልጥ ያየችው ተመሳሳይ ነገር ነው….አራት ወዛቸው የተመጠጠ የለበሱት ልብስ የነታተበ ..በአባቷ ግቢ ውስጥ አትክልቶችን ከሚንከባከቡ ሰራተኞች በላይ ኑሮ የጠበሳቸው ጠና ያሉ ሰውዬ…ቆዳቸው የተሸበሸበ እናት… የ ሀያ አመት ልጅ እግር የምታምር ግን ደግሞ ያልተመቻት ልጃገረዶች..ባለጡንቻ ፈርጣማ እና ባለኮስታራ ፊት ሀያ አምስት ወይም ስድስት የሚሆነው ወጣት ..ጭስ የጠጣና ያረጀ የማዳበሩያ ኮርኒስ ያለው ጠባብ ክፍል…መሬት ላይ የተነጠፈ ፍራሽና ያረጀ በህይወቷ እንኳን ለብሳው አይታው የማታውቀው አይነት ብርድ ልብስ ለብሳ ነበር እራሷን ያገኘችው፡፡ግን እንደዛም ሆኖ የተለየ እና የማታውቀው ቦታ ያለች መስሎ አልተሰማትም….የሆነ ከዘመናት በፊት ታውቀው የነበረ እና ስትናፍቀው የቆየችው ቦታ ተመልሳ እንደመጣች አይነት ስሜት ነው እየተሰማት ያለው
‹‹…የት ነኝ?››
‹‹ልጄ…አሁን ሰላም ነሽ …ትንሽ አደጋ ደርሶብሽ ነው?››
‹‹የምን አደጋ?››
‹‹አሁን ሰላም ነሽ..በውድቅት ለሊት ሞተር ስትነጂ ነበር…ተገልብጠሸ ነው፡፡››
‹‹ሞተር››
‹‹አዎ..ሞተር..ከማን ስትሸሺ ነበር….?እስከአሁን ለፖሊስ አላሳወቅንም…..ይሄውሽ እኔና ቤተሰቦቼ በህይወት ፈተና ጋር ግብግብ ገጥመን በትግል የምንኖር ሰዎች ነን…ከሆነ ወንጀል ጋር የተያያዘ ታሪክ ካለሽ እባክሽ.እኛንም ጣጣ ውስጥ እንዳንገባ ከአሁኑ ንገሪን››ሲል ፊራኦል ተናገረ፡፡
‹‹ምነካህ ልጄ? ልጅቷ ገና አሁን መንቃቷ ነው…ተው እንጂ ነውር ነው›እናትዬው ገሰፁት..አባትዬውም ለባለቤታቸው ድጋፍ በመስጠት‹‹ልጄ አዎ..አሁን ዋናው ያንቺ መትረፍ ነው ፡፡ሌላውን ቀላል ነው…የሰው ልጅ በህይወት ካለ የማያልፈው መከራ የማያሸነፍው የህይወት ትግል የለም..አሁን አንቺ ምንም አታስቢ..እኔነኝ የተባለ ውጌሻ ጠርቼያለሁ፡፡ ወለምታ ወይም ስብራት ነገር ካለሽ ያዩልሻል…ከዛ ካገገምሽ በኋላ ለቤተሰቦችሽ እንደውልላቸውና መጥተው ይወስዱሻል››
በፀሎት ለሊት በውድቅት ለሊት ከቤቷ አምልጣ እንዴት እንደወጣችና ምን እንዳደረገችና አሁን ያለችበት ቤትም የእነማን እንደሆነ ትዝ እያላት ሲመጣ ….የመረጋገትና የደስታ ስሜት ተሰማት
‹‹አመሰግናለሁ…ምንም ወንጀል አልሰራሁም….ፖሊስም እየፈለገኝ አይደለም…አሁን ደክሞኛል ልተኛ..››አለችና መልሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡
‹‹ሰማችሁ አይደል..ምንም ወንጀል አልሰራሁም ብላለች..አሁን ዞር በሉላት …ትንፋሻችሁ እራሱ በሽታ ነው የሚሆናባት››አባትዬው ተቆጡ፡፡
‹‹አባዬ ደግሞ ፣አንተ ሁል ጊዜ ሰው እንዳመንክ ነው.. ሚገርመው ደግሞ ሰዎች ቃላቸውን እያጠፉ አንተን ማሳዘናቸውን አያቆሙም… አንተም ደግሞ ደግመህ ደጋግመህ እነሱን ማመንህን አታቆምም››ፊራኦል ተነጫነጨ፡፡
‹‹ልጄ ገለባ ቢዘሩት አይበቅልም ተጠራጣሪ ሰው አይፀድቅም ይባላል..ያገኘሁትን ሰው ሁሉ በመጠራጠር ህይወቴን ሳሰቃይ ከመኖር እያመንኩ ብከዳ ይሻለኛል…ቢያንስ በማመኔ ምክንያት የሚደርስብኝ ችግር ምክንያቱ እኔ አይደለሁም..››
ፊራኦል በወላጆቹ ውሳኔ ባለመስማማት ‹‹በሉ እሺ እኔ ወደ ስራ ሄጃለሁ፡፡››በማለት ቤተሰቡን ተሰናብቶ ግቢውን ለቆ ሲወጣ በራፍ ላይ ውጌሻዋ ወደውስጥ ስትገባ ተላለፉ፡፡
‹‹ቤቶች አቶ ለሜቻ››ሁሉም ግር ብለው ወጥተው ውጌሻዋን ተቀበሉና ወደውስጥ አስገቧት፡፡
‹‹የትኛው ልጅህ ነች… ለሜቻ?››
‹‹የወንድሜ ልጅ ነች ከድሬደዋ ልትጠይቀኝ መጥታ ነው››
‹‹እና ምን ገጥሟት ነው?››
‹‹ባኮት ከሆነ የሰፈር ልጅ ጋር ሞተር ተፈናጣ ስትሄድ ሞተሩ ተገለበጠባቸውና ትንሽ ተጎዳች..ምን አልባት ስብራት ወይም ወለምታ ይኖራት እንደሆነ ብለን ስለተጠራጠርን ነው ያስቸገርኖት፡፡››
በፀሎት የሚነጋገሩትን ሁሉ አይኖቾን ጨፍና እየሰማች ነው…
‹‹ታዲያ ተኝታለች?››
‹‹አሁን ነቅታ ነበር…እንዴት ነው እንቀስቅሳት?››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠየቁ፡፡
‹‹አይ ቆይ ተዋት ..ህመሙ እራሱ ይቀሰቅሳታል፡፡››አሉና ስሯ ፍራሽ ላይ ተቀመጡ…
‹‹ እስቲ እሱን የከሰል ፍም አቅርቡልኝ››ትዕዛዝ ሰጡ፡፡
ማንደጃው ቀረበላቸው…‹‹ እስኪ አንዳችሁ ኑና የለበሰችውን ልብሷን አውልቁላት…..››ለሊሴ ፈጠን ብላ መጣችና ከላይ የለበሳቸውን ጃኬት… ቦዲ ተራ በተራ አወለቀችላት… በጡት ማስያዣ ብቻ አስቀረቻት ፡፡አንገቷ ላይ ያለው የእጅ መዳፍ የሚያህል አብረቅራቂ እንቁ ፈርጥ ያለበት ጌጥ የሁሉንም አይን በቅፅበት ተቆጣጠረ
….ጆሮዋ ላይም ያንጠለጠለችው የጆሮ ጌጥ ከአንገት ሀብሏ ጋር እንዲናበብ ተደርጎ የተሰራ ለልደት በዓሏ ከአባቷ የተበረከተላት ልዩ አይነት ጌጥ ስለሆን በተለይ የሌሊሳን ትኩረት በደንብ ነው የተቆጣጠረው…ሁሉም ግን አርቴ እንጂ ትክክለኛ ነው ብለው አላሰቡም ነበር፡፡
ውጌሻዋ ቦርሳቸው ውስጥ እጃቸውን ሰደዱና በብልቃጥ ከለጋ ቅቤ ጋር ተለውሶ የተዘጋጀ መዳህኒታቸውን አወጡና ፊት ለፊታቸው አስቀምጠው በሌባ ጣታቸው ዛቅ እያደረጉና በመሀል አጣታቸው ላይ አድርገው በመላ መዳፋቸው ላይ ለቀለቁና ስራቸው በቀረበላቸው የከስል ፍም ላይ ጠጋ አድርገው ሙቀት እንዲያገኝ ካደረጉ በኃላ ከአንገቷ ጀምሮ ትከሻዋን እያሹ መፈተሽ ጀመሩ‹‹ ..ምንም አልሆነችም እስኪ ሱሪዋን አውልቁልኝ››ሌላ ትዕዛዝ ሰጡ..በዚህ ጊዜ አቶ ለሜቻ ከተቀመጡበት ተነሱና ወደውጭ ወጡ..ሴቶቹ እንደምንም
ታጋግዘው የለበሰችውን ጅንስ ሱሪ ከላዮ ላይ አወለቁና በፓንት ብቻ ለውጌሻዋ አስረከቧት
…ውጌሻዋ ተመሳሳዩን እሽት ከጭኖቾ ጀመረው ወደታች መውረድ ጀመሩ…ቀኝ እግሯ ቁርጭምጭሚቷ ጋር ደርሰው ጨበጥ..ጨበጥ ሲያደርጓት ግን ከተኛችበት እንደመብረቅ አጓርታ ተነስታ ቁጭ አለች…ሁሉም በድንጋጤ የሚያደርጉት ጠፋቸው..‹‹አዎ እዚህ ጋር ችግር አለ‹‹አሁን በደንብ አድርጋችሁ ግራና ቀኝ ትከሻዋን ያዟት፡፡››የውጌሻዋን ትዕዛዝ ስትሰማ አይኖቾ በፍራቻ ተጉረጠረጠ፡፡በእድሜዋ መርፌ ለመወጋት እሩሱ በስንት እዝጊዎታና ማባበያ ነው...ታዲያ አሁን እንዲህ ላይቨ በስቃይ ስትፈተን እንባዋ ረገፈ
፡፡እናትና ልጅ ግራና ቀኛ ትከሻዋን አጥብቀው እንዳትነቃነቅ ያዙዋት..ሴትዬዋ እየጨመቁና እያሽከረከሩ ያሾት ጀመር…በህይወቷ ተስምቷት የማያውቀው አይነት ህመም…..ተሰማት..የሆነ መጋዝ ጥርስ ያለው አዞ በሁለት መንጋጋዎች መሀከል እግሮቾን አስገብቶ እያኘካት ነው የመሰላት..እንባዋ ብቻ ሳይሆን ንፍጦም በአፍንጫ ላይ እየተዝረከረከ እንደሆነ ይታወቃታል…ለዛ ግን የምትጨነቅበት ሁኔታ ላይ አይደለችም…..ውጌሻዋ ከ10 ደቂቃ በኃላ የተሰበረውን አጥንት ወደቦታው ከመለሱ በኃላ እንዳይነቃነቅ በቀርከሃ በደንብ አድርገው ካሰሩት በኋላ በፋሻ ጠቅልለው አጠናቀቁ…ከዛ እቃቸውን ሰብስባው ተነሱ…ለሊሴ የራሷን ቢጃማ አለበሰችትና መልሰው አስተኞት፡፡
‹‹እልፍነሽ››
‹‹አቤት እማማ››
‹‹ለሜቻ ድሬደዋ ሀብታም ወንድም አለው እንዴ?››
ወ.ሮ እልፍነሽ ጥያቄው መደናገር ውስጥ አስገባቸው‹‹ለምን ጠየቁኝ?››
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁና አስካለ ግንኙነት ከጀመሩ ከሰባት ወር በኃላ
ግንኙነታቸውን ድንገት የሚያከስም ችግር ተከሰተ፡፡በሁለቱም አእምሮ ያልታሰበበት ቅድመጥንቃቄ ያልተደረገበት አስደንጋጭ ችግር ነው፡፡
ደግሞ ወቅቱ የማትሪክ ውጤት ከዛሬ ነገ ይለቀቃል ተብሎ እየተናፈሰ ስለሆነ አራቱም ጓደኛሞች በጉጉት በምጠበቅበት ወቅት ነበር፡፡ አስካለ ለአላዛር ደወለችለትና በአስቸኳይ እንዲገናኙ እንደምትፈልግ ነገረችው፡፡ከሰፈሯ ብዙም የማይርቅ ካፌ ተቀምጣ ትጠብቀው ጀመር፡፡ብዙም ሳያስጠብቃት እያለከለከ ተገኘ፡፡ እውነተኛ ስሜቱን የሚገልፅ መሸበር ፊቱ ላይ እየታየበት‹‹የእኔ ቆንጆ እንደደወልሽልኝ እየሮጥኩ ነው የመጣሁት.. በአስቸኳይ ፈልግሀለው ስትይኝ ደንግጬ ነበር፡፡››አላት፡፡፡
አስካለ ለእሱ ስሜት እና መሸበር ብዙም ሳትጨነቅ‹‹አዎ …ችግር ተፈጥሯል››አለችው ኩስትርትር እንዳለች፡፡
‹‹የምን ችግር …?ጋሼ ግንኙነታችንን አወቀ እንዴ?››ከፊቷ መኮሳተር እና መገርጣት ከበድ ያለ ነገር እንደተፈጠረ የሚያሳብቅ ነው፡፡ለዛ ነው እንደዛአይነት ጥያቄ የጠየቃት፡፡
‹‹አይ አስከአሁን አላወቀም…››ቅዝዝ እንዳለች መለሰችለት፡፡
‹‹እስከአሁን አላወቀም ስትይ..?ምን ለማለት ነው?››
‹‹ሰሞኑን ሲያዞረኝና ሲያቅለሸልሸኝ ነበር ስልህ ሰምተሀል አይደል?››
‹‹አዎ !!ምነው ባሰብሽ እንዴ?››
‹‹አይ ..ጤና ጣቢያ ሄጄ ነበር…››
‹‹እና ምን አሉሽ..?መድሀኒት አዘዙልሽ?››
‹‹አይ..አርግዤለሁ››
‹‹ምን ..?አርግዤለሁ››
‹‹አዎ አርግዤለሁ››
‹‹‹ወይኔ ጉዳችን..ከእኔ ነው አይደል?››ሲል እራሱን ይዞ በድንጋጤ አይኖቹን እንዳጉረጠረጠ ጠየቃት፡፡‹‹አዎ ካንተ ነው ያረገዝኩት…››ብትለው ምን እንደሚያደርግ አያውቅም፡፡ይሄ በህይወቱ የጋጠመው እውነተኛው ሰበር ዜና ነው፡፡
እሷ ግን እንደዛ አላለችውም፡፡‹‹እሱ ምን ያደርግልሀል…? የጠራሁህ ልጁ ያንተነው ወይም አይደለም ልልህ አይደለም ››
‹‹እና ለምንድነው?››
‹‹ከዛሬ ጀምሮ ግንኙነታችን መቀጠል እንደማንችል እንድታውቅ ነው፡፡››ያላሰበውን ሁለተኛ መርዶ ነገረችው፡፡
‹‹ማለት …ምን አጠፋው?አቅጄና ፈልጌ አይደለም እኮ እንድታርዢ ያደረኩሽ››
‹‹እኔም እንደዛ አልልኩም…አንተ ምንም አላጠፋህም..ግን አሁን እንደምታየው ብቻዬን አይደለሁም …በማህፀኔ ልጅ ይዣለሁ…ለራሴ ሳይሆን ለልጄም ደህንነት መጨነቅ አለብኝ፡፡
እስከዛሬ ካንተ ጋር የቆየሁት ስለማፈቅርህ ነው…ምንም ነገር ቢፈጠር እወጣዋለሁ ብዬ አስቤ ነው…አሁን ግን ነገሮች ተቀይረዋል፡፡በልጄ ላይ እንደዛ ማድረግ አልችልም፡››
አለማየሁ ይሄ ቀን ለዛውም እንደዚህ በቅርብ ይመጣል ብሎ አስቦ አያውቅም ነበር፡፡ይህቺን ሴት በጣም አፍቅሯት ነበር፡፡ከሰሎሜ ቀጥሎ ልቡ የደነገጠባት ሁለተኛዋ ሴት ነች፡፡
ወንድነትን ያጎናፀፈችው ብቸኛዋ ሴት ነች፡፡በህይወቱ አይቶት የማያውቀውን ፍቅር አስኮምኩመዋለች፡፡ብዙ የደስታ ቀናትን እንዲያሳልፍ አድርገዋለች፡፡ በአለም ተወዳጁና ተፈቃሪው ሰው እንደሆነ እንዲሰማው አድርገዋለች..ይህቺን ልጅ እንዲህ በቀላሉ ‹‹በቃ እሺ እንዳልሺው ግንኙነታችንን እናቁም›› ሊላት አልፈለገም፡፡አዎ እሷ የተናገረቻቸው እያንዶንዷቹ ቃላት ከበሳል ሴት የተሰነዘሩና የፀነሰችውን ልጅ ደህንነት ብቻ ሳይሆን የእሱንም የወደፊት ህይወት አደጋ ላይ ላለመጣል አስባበት ያደረገችው ነው፡፡ለዛም እግሯ ስር ተንበርክኮ ሊያመሰግናት ይገባ ነበር፡፡ግን እንደዛ ማድረግ አልቻለም፡፡እንደውም በተቃራኒው ‹‹እባክሽ…ተረጋግተሸ አስቢበት…እኛ መለያየት የለብንም…ከፈለግሽም ተያይዘን መጥፋት እንችላለን፡፡››ሲል በአይኖቹ ጭምር እየተለማመጠ ተማፀናት፡፡
እሷ ግን የተናገረችውን ሁሉ ለቀናት አስባበት..አውርዳና አውጥታ የወሰነችው ስለነበር ከአቋሟ ሽብርክ ልትል አልቻለችም‹‹እባክህ የምታፈቅረኝ ከሆነ ያልኩህን አድርግ….ሁለተኛ ቤት እንዳትማጣ… እንዳትደውልልኝ..መንገድ ላይ እንኳን ብታየኝ ልታናግረኝ እንዳትሞክር፡፡››ብላው እንባዋን እያንጠባጠበች…ለጠጡት ማኪያቶ ክፍያ የሚሆን ድፍን መቶ ብር ጠረጴዛ ላይ አስቀምጣ በተቀመጠበት ጥላው ሄደች፡፡
አለማየሁም ጓደኞቹ ግራ እስኪገባቸው ድረስ ለአንድ ወር ነበር ያዘነው፡፡ለሌላ የማይነግሩት የብቻ ሀዘን ደግሞ ውስጥን እንዴት እንደሚበላ የደረሰበት ነው የሚያውቀው፡፡በጣም ነበር የተጎዳው፡፡የሀዘኑ ምንጭ ከእሷ ጋር ያለው ግንኙነት ስለተቋረተ ብቻ አይደለም..እሱንማ ትክክለኛ ቀኑን አይወቅ እንጂ አንድ ቀን እንደሚሆን ከበፊቱ ያውቅ ነበር፡፡በጣም የጎዳው የተፈጠረው ሁኔታ ነው፡፡በመሀከላቸው ልጅ መፈጠሩ….ልጁ በተሳሳተ አባት እጅ ማደጉ….
በጣም የሚገርመው ደግሞ ከገባበት ደባሪ ሀዘን ሳይወጣ በተጨማሪ ሌላ ህይወት መንሸራተት ገጠመው ፡፡ የማትሪክ ውጤት ተነግሮ ከሁሴን በስተቀር እሱን ጨምሮ ሁሉም ጓደኞቹ ዝቅተኛ ውጤት ማምጣታቸው ታወቀ፡፡እርግጥ ከአራቱ ጓደኛሞች ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ሁሴን ብቻ ማምጣቱ ከበፊቱም የሚጠበቅና ሚገመት ነበር፡፡ቢሆንም የቁርጡ ቀን መጥቶ ሁሉም በግልፅ ሲታወቅ ቅሬታ መፍጠሩ አይቀርም፤ቢሆንም ለዚህኛው ሀዘን አብረውት የሚያዝኑ ጓደኞች አሉት፡፡የእሱ መከፋትን እነሱም ሚከፉት ስለሆነ እርስ በርስ ለመፅናናት ቀላል ነው፡፡እና እንደመጀመሪያው ችግር አልከበደውም፡፡
ሁሴን ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ደርሶት ደግሰውና መርቀው ከላኩት በኋላ እነሱ ምን ማድረግ እንዳለባቸው መማከር ጀመሩ..እርግጥ ከበፊቱም ጀምሮ አላዛር የራሱ ሱቅ ያለውና በንግድ የሚተዳደር ስለሆነ ከእነሱ በተለይ የሚፅናናበት እና ሚመካበት ነገር ስላለው ነገሮች ብዙም አላስጨነቁትም….አንድ ቤት እንደእህትና ወንድም የሚኖሩት አለማየውና ሰሎሜ ግን ምንም አማራጭ የላቸውም..በተለይ አለማየሁ ከገጠመው የፍቅር ስብራት ጋር አንድ ላይ ተጨማምሮ ተራራ የተሸከመ አይነት ስሜት ነበር እየተሰማው ያለው፡፡ ቢሆንም እንደምንም በጓደኞቹ ጎትጓችነት እንደምንም ከቁዘማ ወጥቶ ለገጠሙት ችግሮች መፍትሄ መፈለግ እንዳለበት በማመን መንቀሳቀስ ጀመረ….፡፡
በድንገት ወደህይወቱ ገብታ የፍቅር አልኮል ስትግተው የሰነበተችው የጓደኛው የአላዛር የእንጀራ እናት ‹‹አርግዤለሁ እና ከአሁን ወዲህ አልፈልግህም ››ማለቷ ከፈጠረበት ድባቴ መች ሙሉ ለሙሉ ማገገም እንደሚችል አያውቅም ፡፡ፈጽሞ ከአእምሮው ሊፍቀው የሚችል ሁኔታ አልሆነለትም፡፡በ19 አመቱ የልጅ አባት ከመሆኑም በላይ ከባለትዳር ሴት መወስለቱ በአሳዳጊው እቴቴ ዘንድ እንዲሁም በሚያፈቅራት በልጇ ሰሎሜ ዘንድ ምን አይነት ስሜት እንዲሚፈጥር እያሰበ እየተሳቀቀ ነው፡፡ደግነቱ ልጅቷ ለራሷ ደህንነት ስትል ሚስጥሩን ላለመናገር ወስናለች…በዛም የተወሰነ እፎይታ ተስምቷታል ፡፡ከአስካለ ጋር የነበረው አጭር ግን ደግሞ ጣፋጭ ፍቅር ግንኙነት በአጭሩ እና ባልሆነ መንገድ መቀጨቱ አሳዛኝ ቢሆንም አሁንም ዋናው የህይወት ህልሙ ሰሎሜ ስላለች ለእሷ በቂ ሰው ሆኖ መገኘት እንዳለበት አሰበ….ለዚህም ይረዳው ዘንድ እንደምንም ብሎ ትምህርቱን በመጠኑም ቢሆን ወደፊት መግፋት እንዳለበት ስለወሰነ...ከአላዛርና ከራሷ ከሰሎሜ ጋር በመመካከር ሶስቱም የሞያ ትምህርት ለመማር ተግባረእድ ኮሌጅ ተመዘገቡ…በዚህም የተወሰነ የመንፈስ መነቃቃት አሳየ ….ትምህርቱ ከዛሬ ነገ ይጀመራል በሚል ተስፋ መጠባበቅ ጀመሩ፡፡ ግን ደግሞ አንዳንዴ ሕይወት ከፊት ለፊታችን እንቅፋት መደርደር ከጀመረች
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አለማየሁና አስካለ ግንኙነት ከጀመሩ ከሰባት ወር በኃላ
ግንኙነታቸውን ድንገት የሚያከስም ችግር ተከሰተ፡፡በሁለቱም አእምሮ ያልታሰበበት ቅድመጥንቃቄ ያልተደረገበት አስደንጋጭ ችግር ነው፡፡
ደግሞ ወቅቱ የማትሪክ ውጤት ከዛሬ ነገ ይለቀቃል ተብሎ እየተናፈሰ ስለሆነ አራቱም ጓደኛሞች በጉጉት በምጠበቅበት ወቅት ነበር፡፡ አስካለ ለአላዛር ደወለችለትና በአስቸኳይ እንዲገናኙ እንደምትፈልግ ነገረችው፡፡ከሰፈሯ ብዙም የማይርቅ ካፌ ተቀምጣ ትጠብቀው ጀመር፡፡ብዙም ሳያስጠብቃት እያለከለከ ተገኘ፡፡ እውነተኛ ስሜቱን የሚገልፅ መሸበር ፊቱ ላይ እየታየበት‹‹የእኔ ቆንጆ እንደደወልሽልኝ እየሮጥኩ ነው የመጣሁት.. በአስቸኳይ ፈልግሀለው ስትይኝ ደንግጬ ነበር፡፡››አላት፡፡፡
አስካለ ለእሱ ስሜት እና መሸበር ብዙም ሳትጨነቅ‹‹አዎ …ችግር ተፈጥሯል››አለችው ኩስትርትር እንዳለች፡፡
‹‹የምን ችግር …?ጋሼ ግንኙነታችንን አወቀ እንዴ?››ከፊቷ መኮሳተር እና መገርጣት ከበድ ያለ ነገር እንደተፈጠረ የሚያሳብቅ ነው፡፡ለዛ ነው እንደዛአይነት ጥያቄ የጠየቃት፡፡
‹‹አይ አስከአሁን አላወቀም…››ቅዝዝ እንዳለች መለሰችለት፡፡
‹‹እስከአሁን አላወቀም ስትይ..?ምን ለማለት ነው?››
‹‹ሰሞኑን ሲያዞረኝና ሲያቅለሸልሸኝ ነበር ስልህ ሰምተሀል አይደል?››
‹‹አዎ !!ምነው ባሰብሽ እንዴ?››
‹‹አይ ..ጤና ጣቢያ ሄጄ ነበር…››
‹‹እና ምን አሉሽ..?መድሀኒት አዘዙልሽ?››
‹‹አይ..አርግዤለሁ››
‹‹ምን ..?አርግዤለሁ››
‹‹አዎ አርግዤለሁ››
‹‹‹ወይኔ ጉዳችን..ከእኔ ነው አይደል?››ሲል እራሱን ይዞ በድንጋጤ አይኖቹን እንዳጉረጠረጠ ጠየቃት፡፡‹‹አዎ ካንተ ነው ያረገዝኩት…››ብትለው ምን እንደሚያደርግ አያውቅም፡፡ይሄ በህይወቱ የጋጠመው እውነተኛው ሰበር ዜና ነው፡፡
እሷ ግን እንደዛ አላለችውም፡፡‹‹እሱ ምን ያደርግልሀል…? የጠራሁህ ልጁ ያንተነው ወይም አይደለም ልልህ አይደለም ››
‹‹እና ለምንድነው?››
‹‹ከዛሬ ጀምሮ ግንኙነታችን መቀጠል እንደማንችል እንድታውቅ ነው፡፡››ያላሰበውን ሁለተኛ መርዶ ነገረችው፡፡
‹‹ማለት …ምን አጠፋው?አቅጄና ፈልጌ አይደለም እኮ እንድታርዢ ያደረኩሽ››
‹‹እኔም እንደዛ አልልኩም…አንተ ምንም አላጠፋህም..ግን አሁን እንደምታየው ብቻዬን አይደለሁም …በማህፀኔ ልጅ ይዣለሁ…ለራሴ ሳይሆን ለልጄም ደህንነት መጨነቅ አለብኝ፡፡
እስከዛሬ ካንተ ጋር የቆየሁት ስለማፈቅርህ ነው…ምንም ነገር ቢፈጠር እወጣዋለሁ ብዬ አስቤ ነው…አሁን ግን ነገሮች ተቀይረዋል፡፡በልጄ ላይ እንደዛ ማድረግ አልችልም፡››
አለማየሁ ይሄ ቀን ለዛውም እንደዚህ በቅርብ ይመጣል ብሎ አስቦ አያውቅም ነበር፡፡ይህቺን ሴት በጣም አፍቅሯት ነበር፡፡ከሰሎሜ ቀጥሎ ልቡ የደነገጠባት ሁለተኛዋ ሴት ነች፡፡
ወንድነትን ያጎናፀፈችው ብቸኛዋ ሴት ነች፡፡በህይወቱ አይቶት የማያውቀውን ፍቅር አስኮምኩመዋለች፡፡ብዙ የደስታ ቀናትን እንዲያሳልፍ አድርገዋለች፡፡ በአለም ተወዳጁና ተፈቃሪው ሰው እንደሆነ እንዲሰማው አድርገዋለች..ይህቺን ልጅ እንዲህ በቀላሉ ‹‹በቃ እሺ እንዳልሺው ግንኙነታችንን እናቁም›› ሊላት አልፈለገም፡፡አዎ እሷ የተናገረቻቸው እያንዶንዷቹ ቃላት ከበሳል ሴት የተሰነዘሩና የፀነሰችውን ልጅ ደህንነት ብቻ ሳይሆን የእሱንም የወደፊት ህይወት አደጋ ላይ ላለመጣል አስባበት ያደረገችው ነው፡፡ለዛም እግሯ ስር ተንበርክኮ ሊያመሰግናት ይገባ ነበር፡፡ግን እንደዛ ማድረግ አልቻለም፡፡እንደውም በተቃራኒው ‹‹እባክሽ…ተረጋግተሸ አስቢበት…እኛ መለያየት የለብንም…ከፈለግሽም ተያይዘን መጥፋት እንችላለን፡፡››ሲል በአይኖቹ ጭምር እየተለማመጠ ተማፀናት፡፡
እሷ ግን የተናገረችውን ሁሉ ለቀናት አስባበት..አውርዳና አውጥታ የወሰነችው ስለነበር ከአቋሟ ሽብርክ ልትል አልቻለችም‹‹እባክህ የምታፈቅረኝ ከሆነ ያልኩህን አድርግ….ሁለተኛ ቤት እንዳትማጣ… እንዳትደውልልኝ..መንገድ ላይ እንኳን ብታየኝ ልታናግረኝ እንዳትሞክር፡፡››ብላው እንባዋን እያንጠባጠበች…ለጠጡት ማኪያቶ ክፍያ የሚሆን ድፍን መቶ ብር ጠረጴዛ ላይ አስቀምጣ በተቀመጠበት ጥላው ሄደች፡፡
አለማየሁም ጓደኞቹ ግራ እስኪገባቸው ድረስ ለአንድ ወር ነበር ያዘነው፡፡ለሌላ የማይነግሩት የብቻ ሀዘን ደግሞ ውስጥን እንዴት እንደሚበላ የደረሰበት ነው የሚያውቀው፡፡በጣም ነበር የተጎዳው፡፡የሀዘኑ ምንጭ ከእሷ ጋር ያለው ግንኙነት ስለተቋረተ ብቻ አይደለም..እሱንማ ትክክለኛ ቀኑን አይወቅ እንጂ አንድ ቀን እንደሚሆን ከበፊቱ ያውቅ ነበር፡፡በጣም የጎዳው የተፈጠረው ሁኔታ ነው፡፡በመሀከላቸው ልጅ መፈጠሩ….ልጁ በተሳሳተ አባት እጅ ማደጉ….
በጣም የሚገርመው ደግሞ ከገባበት ደባሪ ሀዘን ሳይወጣ በተጨማሪ ሌላ ህይወት መንሸራተት ገጠመው ፡፡ የማትሪክ ውጤት ተነግሮ ከሁሴን በስተቀር እሱን ጨምሮ ሁሉም ጓደኞቹ ዝቅተኛ ውጤት ማምጣታቸው ታወቀ፡፡እርግጥ ከአራቱ ጓደኛሞች ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ሁሴን ብቻ ማምጣቱ ከበፊቱም የሚጠበቅና ሚገመት ነበር፡፡ቢሆንም የቁርጡ ቀን መጥቶ ሁሉም በግልፅ ሲታወቅ ቅሬታ መፍጠሩ አይቀርም፤ቢሆንም ለዚህኛው ሀዘን አብረውት የሚያዝኑ ጓደኞች አሉት፡፡የእሱ መከፋትን እነሱም ሚከፉት ስለሆነ እርስ በርስ ለመፅናናት ቀላል ነው፡፡እና እንደመጀመሪያው ችግር አልከበደውም፡፡
ሁሴን ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ደርሶት ደግሰውና መርቀው ከላኩት በኋላ እነሱ ምን ማድረግ እንዳለባቸው መማከር ጀመሩ..እርግጥ ከበፊቱም ጀምሮ አላዛር የራሱ ሱቅ ያለውና በንግድ የሚተዳደር ስለሆነ ከእነሱ በተለይ የሚፅናናበት እና ሚመካበት ነገር ስላለው ነገሮች ብዙም አላስጨነቁትም….አንድ ቤት እንደእህትና ወንድም የሚኖሩት አለማየውና ሰሎሜ ግን ምንም አማራጭ የላቸውም..በተለይ አለማየሁ ከገጠመው የፍቅር ስብራት ጋር አንድ ላይ ተጨማምሮ ተራራ የተሸከመ አይነት ስሜት ነበር እየተሰማው ያለው፡፡ ቢሆንም እንደምንም በጓደኞቹ ጎትጓችነት እንደምንም ከቁዘማ ወጥቶ ለገጠሙት ችግሮች መፍትሄ መፈለግ እንዳለበት በማመን መንቀሳቀስ ጀመረ….፡፡
በድንገት ወደህይወቱ ገብታ የፍቅር አልኮል ስትግተው የሰነበተችው የጓደኛው የአላዛር የእንጀራ እናት ‹‹አርግዤለሁ እና ከአሁን ወዲህ አልፈልግህም ››ማለቷ ከፈጠረበት ድባቴ መች ሙሉ ለሙሉ ማገገም እንደሚችል አያውቅም ፡፡ፈጽሞ ከአእምሮው ሊፍቀው የሚችል ሁኔታ አልሆነለትም፡፡በ19 አመቱ የልጅ አባት ከመሆኑም በላይ ከባለትዳር ሴት መወስለቱ በአሳዳጊው እቴቴ ዘንድ እንዲሁም በሚያፈቅራት በልጇ ሰሎሜ ዘንድ ምን አይነት ስሜት እንዲሚፈጥር እያሰበ እየተሳቀቀ ነው፡፡ደግነቱ ልጅቷ ለራሷ ደህንነት ስትል ሚስጥሩን ላለመናገር ወስናለች…በዛም የተወሰነ እፎይታ ተስምቷታል ፡፡ከአስካለ ጋር የነበረው አጭር ግን ደግሞ ጣፋጭ ፍቅር ግንኙነት በአጭሩ እና ባልሆነ መንገድ መቀጨቱ አሳዛኝ ቢሆንም አሁንም ዋናው የህይወት ህልሙ ሰሎሜ ስላለች ለእሷ በቂ ሰው ሆኖ መገኘት እንዳለበት አሰበ….ለዚህም ይረዳው ዘንድ እንደምንም ብሎ ትምህርቱን በመጠኑም ቢሆን ወደፊት መግፋት እንዳለበት ስለወሰነ...ከአላዛርና ከራሷ ከሰሎሜ ጋር በመመካከር ሶስቱም የሞያ ትምህርት ለመማር ተግባረእድ ኮሌጅ ተመዘገቡ…በዚህም የተወሰነ የመንፈስ መነቃቃት አሳየ ….ትምህርቱ ከዛሬ ነገ ይጀመራል በሚል ተስፋ መጠባበቅ ጀመሩ፡፡ ግን ደግሞ አንዳንዴ ሕይወት ከፊት ለፊታችን እንቅፋት መደርደር ከጀመረች