#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ድህረ_ታሪክ
፡
፡
#አዲስ_ፍቅር_አዲስ_ሕይወት
አንድ የተሰበረ ልብ ለማገገም ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል ብሎ ለመተንበይ ያዳግታል፤ እኔ ግን ተባርኬያለሁ፡- በእግዚአብሔር እርዳታ ልቤ ከሁለት ዓመት በኋላ ሌላ ለማፍቀር ችሏል፡፡ ስድን ግን የኖርኩት ዝምተኛና አመዛዛኝ ሕይወት ነው ፡፡በተመድ እየሠራሁና ከሳራ ቤተሰብ ጋር እየኖርኩ በትርፍ ጊዜዬ ኪጋሊ በሚገኝ አንድ የእጓለማውታ ማሳደጊያ በደርዘኖች ለሚቆጠሩ የተሸበሩ ብቸኛ ልጆች በታላቅ እህትነት በማገልገል በበጎ ፈቃደኝነት ሥራ አሳለፍኩ፡፡ በፈረንሳይ ምሽግ እንከባከባቸው የነበሩትን ሁለት ወንድማማቾች ሥራዬ ብዬ ብፈልጋቸውም ላገኛቸው አልቻልኩም፡፡ ይሁን እንጂ ሌሎች ብዙ ፍቅር ፈላጊ ወጣቶችን አግኝቻለሁ፡፡ በ1995 መጨረሻ ከኤይማብል ጋር ተገናኘሁ፡፡ ነጻ የትምህርት ዕድል የሰጠው አካል በሩዋንዳ ሰላም ተመልሷል ብሎ ስላመነ ወደ አገሩ የሚመጣበትን የአየር መጓጓዣ ወጪ ሸፈነለት፡፡ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ጊዜ ተጻጽፈናል፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያትም በስልክ አውርተናል፡፡ በአካል ለመገናኘት ግን በመንፈስ አልተዘጋጀንም፡፡ በአየር ማረፊያው የተገናኘንበትን ሁኔታ መቼም አልረሳውም፡፡ ልቦቻችንን ከክፉ እየጠበቅን ይመስል ስሜታችን ፈንቅሎ በመውጣት ወይም እንባ በመራጨት ፈንታ አቀባበሉ በስሱ ተከናወነ፡፡ ተቃቀፍን፣ ተሳሳምን፤ እኔ የእርሱን፣ እርሱም የኔን ህመም ላለመንካት ግን ተፈራርተን ጥንቃቄ አደረግን፡፡ ዓይን ለዓይን ለመተያየት ተፈራራን፡፡ እውነተኛ ስሜታችን ከወጣ መቆጣጠር እንደሚያቅተን አውቀን ከበደን፡፡ ማልቀስ ከጀመርን ማቆሚያ እንደሌለን ገብቶናል፡፡
ወንድሜና እኔ ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ምግብ ቤት ሄደን ራት እየበላን ስለ እርሱ ትምህርትና ስለኔ ሥራ እያወራንና በጓደኞቼም ቀልዶች እየሣቅን እናስመስል ያዝን፡፡ በዚያ ሌሊት ግን ብቻዬን መኝታዬ ላይ ሆኜ እንባዬን ዘረገፍኩት፡፡ ወንድሜም እንዲሁ እንዳደረገ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን አብሮ መሆኑ ይበልጥ ቀለለን፡፡ ምንም እንኳን እርስ በርስ መተያየቱ የቤተሰባችንን አሳዛኝ ፍጻሜ አሰቃቂ ትውስታ የሚቀሰቅስብን ቢሆንም በጣም ስለምንዋደድ አንዳችን በሌላችን መኖር ምቾት ተሰምቶናል፡፡ ህመሙን ለመቋቋም የሚያግዘኝን ጥንካሬ እንዳገኘሁ ልነግረውና ላጽናናውም ፈልጌያለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የማያጽናኑት ዓይነት እንዳልሆነ ወዲያውኑ ታወቀኝ፡፡ ከአፍታ በኋላም በቤተሰባችን ስለተከሰተው ሰቆቃ ላለማንሳት ሳንነጋገር እንደተስማማን ገባን፡፡ የቤተሰባችንን አባላት ሁሉ በስም ጠቃቀስን፡፡ ያኔም ቢሆን አሁንም በሕይወት እንዳሉ አድርገን ነበር ያወራነው - የምንቋቋምበት ብቸኛው መንገዳችን ይህ ነው፡፡ ለቀጣዮቹም ሁለት ዓመታት በደብዳቤና በስልክ እንደዚያው ስናደርግ ቆየን፡፡ ኤይማብል የእንስሳት ሕክምና የድህረ ምረቃ መርሃ-ግብሩን ጨርሶ ወደ ኪጋሊ ሲመለስም ሁኔታው አልተቀየረም፡፡ በየቀኑ በአካል ብንገናኝም ስለ ዘር ጭፍጨፋው የምናወራው አንድ የሆነ ሰው ላይ የተከሰተ ይመስል እንዲያው በደምሳሳው ነው፡፡ የእማማንና የዳማሲንን መቃብርም ሲያይ እንኳን እንዳካሂደው አልጠየቀኝም፤ ብቻውን ሄደ፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያው እንዲሁ አለን፡፡ ኤይማብል አሁንም የሚኖረው ኪጋሊ ነው፤ ስኬታማ ሐኪም ሲሆን ቆንጅዬ ሚስትና ልጆች አሉት፡፡ እርስ በርሳችን በጣም እንዋደዳለን፤ ከመቼውም በላይ ቅርርብ አለን፡፡ በየጊዜው እንደዋወላለን፤ ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜም እንጻጻፋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላም ስለቤተሰባችን ስንነጋገር ‹ነበር› አንልም፡፡ ትዝታቸውን ህያው አድርጎ ማቆያ መንገዳችን ይህ ነው ብዬ እገምታለሁ፡፡
ብዙ ምሽቶቼን በአቅራቢያዬ ባለና ሁለተኛ ቤቴ ሆኖ በነበረው በጀስዊቶች ማእከል በጸሎትና ተመስጦ ተጠምጄ አሳልፋሁ፡፡ በተደበቅሁባቸው ረጅም ወራት ወቅት ያዳነኝን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረኝን የጠበቀ ቁርኝቴን በድጋሚ የጀመርኩት በነዚያ ርጭ ባሉ ስፍራዎች ነው፡፡
ልቤ ቀስ በቀስ ሲያገግምልኝ የወደፊቱን ሕይወቴን አብሬ የሚጋራ አንድ ልዩ የራሴ የምለው ሰውና የምንከባከበው ቤተሰብ ማለም ጀመርኩ፡፡ ግን ሐሳብ ገባኝ … ከዮሃንስ ጋር የነበረኝን ሁኔታ አስታወስኩና በቀላሉ ሊሰበር የሚችለውን ልቤን የትም ለማይደርስና በሚያሳምም መልኩ ለሚቋጭ ግንኙነት ላለመስጠት ወሰንኩ፡፡ ስለዚህ ችግር ወይም ፈተና በሚያጋጥመኝ ጊዜ ሁሉ እንደማደርገው የአምላክን እገዛ ጠየቅሁ፡፡ በገነት የሚሆን ጋብቻ ከፈለግሁ ከአምላኬ በተሻለ የሚኩለኝና የሚድረኝ ከቶ ማን ይኖራል?
መጽሐፍ ቅዱስ ከጠየቅን እንደምናገኝ ይነግረናል፤ በእርግጥም ያንን አደረግሁ፡፡ እግዚአብሔርን የማልመውን ሰው እንዲያመጣልኝ ጠየቅሁት፡፡ ራሴን ማጭበርበር አልፈልግሁም - እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የምፈልገው ሰው ምን ዓይነት እንደሆነ በጣም ግልጽ ማድረግ ነበረብኝ፡፡ ስለሆነም ወረቀት ይዤ ተቀመጥኩና ላገባው የምፈልገውን ሰው ፊት ነደፍኩ፡፡ ከዚያም ቁመቱንና ሌሎቹን ገጽታዎቹን ዘረዘርኩ፡፡ ጠንካራ ማንነትና ምቹ ስብዕና ያለው፣ ደግ፣ አፍቃሪና ርህሩህ፣ ተጨዋች፣ ምግባረመልካም፣ ማንነቴን የሚወድልኝ፣ እንደኔ ልጆችን የሚያፈቅርና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን የሚወድ ሰው ይሰጠኝ ዘንድ ጠየቅሁ፡፡
ለእግዚአብሔር ቀን አልቆረጥኩለትም፡፡ በዘር፣ በዜግነት ወይንም የቆዳ ቀለም ላይም ምንም ገደብ አልጣልኩ፡፡ በዓለም ላይ ከአምስት ቢሊየን በላይ ሰዎች እንደመኖራቸው - ጌታዬ የሕይወቴን አጋር የሚልክበትና እኔም የምጠብቅበት አግባብ ያለው የቆይታ ጊዜ ስድስት ወራት እንዲሆን አቀድኩ፡፡ አንድ ማስጠንቀቂያንም ጨመርኩ፡- ድንግል ማርያምን እጅግ ስለምወዳት እግዚአብሔር ከእምነቴ ተመሳሳይ የሆነ ባል ቢልክልኝ እንደሚሻል ነገርኩት፡፡ በሃይማኖት ሳቢያ በትዳሬ ምንም ዓይነት ውጥረት እንደማይኖር ማረጋገጥ እንዲሁም ባሌ እግዚአብሔርን እኔ በማመልከው መልኩ እንዲያመልክ ፈለግሁ፡፡
ምን እንደምፈልግ በትክክል ካወቅሁ በኋላ ፍላጎቴን አልመው ጀመር፡፡ ጌታ የተመኘሁትን ባርኮ እንደሚሰጠኝ፣ የልቤ መሻት እንደሚሆንልኝና የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነ አምኜ ሁሉንም ለእርሱ ተውኩት፡፡ ሂደቱን ለማፋጠን የአባቴን ቀይና ነጭ መቁጠሪያ አወጣሁና ባሌ እንዲመጣልኝ መጸለይ ጀመርኩ፡፡ ከሦስት ወራት በኋላም መጣልኝ፡- ከእግዚአብሔር የተላከውና የተመድ የሸለመኝ አቶ ብርያን ብላክ ከአሜሪካ ድረስ ከተፍ አለ! የነገሩ መገጣጠም ደሞ ብርያን ወደ ሀገሪቱ የመጣው የዘር ማጥፋቱን በማቀድ የተሳተፉትን ለፍርድ ለማቅረብ የሚጥረውን የተመዱን ዓለም አቀፍ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት በማቋቋሙ ሂደት ለማገዝ ሆኖ እርፍ፡፡ ብርያን ለተመድ ለብዙ ዓመታት ስለሠራ ገዳዮቹን ፍትሃዊ ቅጣት እንዲያገኙ የሚያደርገው የተልዕኮው አካል በመሆኑ ይደሰታል፡፡ በግሌ እርሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ ነው፡፡
ብርያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ ግቢ ሳየው በትክክል እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የጠየቅሁትን ሰውዬ መሰለኝ፡፡ በኋላ በአዳራሹ ሳልፈውና በዓይኖቹ የነበረውን ጥልቅ እርጋታ ሳይ እርሱ እንደሆነ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ግን በእግዚአብሔር እምነቴን ስላደረግሁ ብርያንን ወደኔ እንዲያመጣው ጠበቅሁት አመጣልኛ ብርያን አብረን እንድንዝናና ጋብዞኝ ግሩም ጊዜ አሳለፍን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
#ድህረ_ታሪክ
፡
፡
#አዲስ_ፍቅር_አዲስ_ሕይወት
አንድ የተሰበረ ልብ ለማገገም ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል ብሎ ለመተንበይ ያዳግታል፤ እኔ ግን ተባርኬያለሁ፡- በእግዚአብሔር እርዳታ ልቤ ከሁለት ዓመት በኋላ ሌላ ለማፍቀር ችሏል፡፡ ስድን ግን የኖርኩት ዝምተኛና አመዛዛኝ ሕይወት ነው ፡፡በተመድ እየሠራሁና ከሳራ ቤተሰብ ጋር እየኖርኩ በትርፍ ጊዜዬ ኪጋሊ በሚገኝ አንድ የእጓለማውታ ማሳደጊያ በደርዘኖች ለሚቆጠሩ የተሸበሩ ብቸኛ ልጆች በታላቅ እህትነት በማገልገል በበጎ ፈቃደኝነት ሥራ አሳለፍኩ፡፡ በፈረንሳይ ምሽግ እንከባከባቸው የነበሩትን ሁለት ወንድማማቾች ሥራዬ ብዬ ብፈልጋቸውም ላገኛቸው አልቻልኩም፡፡ ይሁን እንጂ ሌሎች ብዙ ፍቅር ፈላጊ ወጣቶችን አግኝቻለሁ፡፡ በ1995 መጨረሻ ከኤይማብል ጋር ተገናኘሁ፡፡ ነጻ የትምህርት ዕድል የሰጠው አካል በሩዋንዳ ሰላም ተመልሷል ብሎ ስላመነ ወደ አገሩ የሚመጣበትን የአየር መጓጓዣ ወጪ ሸፈነለት፡፡ ከመምጣቱ በፊት ብዙ ጊዜ ተጻጽፈናል፡፡ ለተወሰኑ ጊዜያትም በስልክ አውርተናል፡፡ በአካል ለመገናኘት ግን በመንፈስ አልተዘጋጀንም፡፡ በአየር ማረፊያው የተገናኘንበትን ሁኔታ መቼም አልረሳውም፡፡ ልቦቻችንን ከክፉ እየጠበቅን ይመስል ስሜታችን ፈንቅሎ በመውጣት ወይም እንባ በመራጨት ፈንታ አቀባበሉ በስሱ ተከናወነ፡፡ ተቃቀፍን፣ ተሳሳምን፤ እኔ የእርሱን፣ እርሱም የኔን ህመም ላለመንካት ግን ተፈራርተን ጥንቃቄ አደረግን፡፡ ዓይን ለዓይን ለመተያየት ተፈራራን፡፡ እውነተኛ ስሜታችን ከወጣ መቆጣጠር እንደሚያቅተን አውቀን ከበደን፡፡ ማልቀስ ከጀመርን ማቆሚያ እንደሌለን ገብቶናል፡፡
ወንድሜና እኔ ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ምግብ ቤት ሄደን ራት እየበላን ስለ እርሱ ትምህርትና ስለኔ ሥራ እያወራንና በጓደኞቼም ቀልዶች እየሣቅን እናስመስል ያዝን፡፡ በዚያ ሌሊት ግን ብቻዬን መኝታዬ ላይ ሆኜ እንባዬን ዘረገፍኩት፡፡ ወንድሜም እንዲሁ እንዳደረገ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን አብሮ መሆኑ ይበልጥ ቀለለን፡፡ ምንም እንኳን እርስ በርስ መተያየቱ የቤተሰባችንን አሳዛኝ ፍጻሜ አሰቃቂ ትውስታ የሚቀሰቅስብን ቢሆንም በጣም ስለምንዋደድ አንዳችን በሌላችን መኖር ምቾት ተሰምቶናል፡፡ ህመሙን ለመቋቋም የሚያግዘኝን ጥንካሬ እንዳገኘሁ ልነግረውና ላጽናናውም ፈልጌያለሁ፡፡ ይሁን እንጂ የማያጽናኑት ዓይነት እንዳልሆነ ወዲያውኑ ታወቀኝ፡፡ ከአፍታ በኋላም በቤተሰባችን ስለተከሰተው ሰቆቃ ላለማንሳት ሳንነጋገር እንደተስማማን ገባን፡፡ የቤተሰባችንን አባላት ሁሉ በስም ጠቃቀስን፡፡ ያኔም ቢሆን አሁንም በሕይወት እንዳሉ አድርገን ነበር ያወራነው - የምንቋቋምበት ብቸኛው መንገዳችን ይህ ነው፡፡ ለቀጣዮቹም ሁለት ዓመታት በደብዳቤና በስልክ እንደዚያው ስናደርግ ቆየን፡፡ ኤይማብል የእንስሳት ሕክምና የድህረ ምረቃ መርሃ-ግብሩን ጨርሶ ወደ ኪጋሊ ሲመለስም ሁኔታው አልተቀየረም፡፡ በየቀኑ በአካል ብንገናኝም ስለ ዘር ጭፍጨፋው የምናወራው አንድ የሆነ ሰው ላይ የተከሰተ ይመስል እንዲያው በደምሳሳው ነው፡፡ የእማማንና የዳማሲንን መቃብርም ሲያይ እንኳን እንዳካሂደው አልጠየቀኝም፤ ብቻውን ሄደ፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያው እንዲሁ አለን፡፡ ኤይማብል አሁንም የሚኖረው ኪጋሊ ነው፤ ስኬታማ ሐኪም ሲሆን ቆንጅዬ ሚስትና ልጆች አሉት፡፡ እርስ በርሳችን በጣም እንዋደዳለን፤ ከመቼውም በላይ ቅርርብ አለን፡፡ በየጊዜው እንደዋወላለን፤ ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜም እንጻጻፋለን፡፡ አሁንም ቢሆን ከእነዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላም ስለቤተሰባችን ስንነጋገር ‹ነበር› አንልም፡፡ ትዝታቸውን ህያው አድርጎ ማቆያ መንገዳችን ይህ ነው ብዬ እገምታለሁ፡፡
ብዙ ምሽቶቼን በአቅራቢያዬ ባለና ሁለተኛ ቤቴ ሆኖ በነበረው በጀስዊቶች ማእከል በጸሎትና ተመስጦ ተጠምጄ አሳልፋሁ፡፡ በተደበቅሁባቸው ረጅም ወራት ወቅት ያዳነኝን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረኝን የጠበቀ ቁርኝቴን በድጋሚ የጀመርኩት በነዚያ ርጭ ባሉ ስፍራዎች ነው፡፡
ልቤ ቀስ በቀስ ሲያገግምልኝ የወደፊቱን ሕይወቴን አብሬ የሚጋራ አንድ ልዩ የራሴ የምለው ሰውና የምንከባከበው ቤተሰብ ማለም ጀመርኩ፡፡ ግን ሐሳብ ገባኝ … ከዮሃንስ ጋር የነበረኝን ሁኔታ አስታወስኩና በቀላሉ ሊሰበር የሚችለውን ልቤን የትም ለማይደርስና በሚያሳምም መልኩ ለሚቋጭ ግንኙነት ላለመስጠት ወሰንኩ፡፡ ስለዚህ ችግር ወይም ፈተና በሚያጋጥመኝ ጊዜ ሁሉ እንደማደርገው የአምላክን እገዛ ጠየቅሁ፡፡ በገነት የሚሆን ጋብቻ ከፈለግሁ ከአምላኬ በተሻለ የሚኩለኝና የሚድረኝ ከቶ ማን ይኖራል?
መጽሐፍ ቅዱስ ከጠየቅን እንደምናገኝ ይነግረናል፤ በእርግጥም ያንን አደረግሁ፡፡ እግዚአብሔርን የማልመውን ሰው እንዲያመጣልኝ ጠየቅሁት፡፡ ራሴን ማጭበርበር አልፈልግሁም - እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የምፈልገው ሰው ምን ዓይነት እንደሆነ በጣም ግልጽ ማድረግ ነበረብኝ፡፡ ስለሆነም ወረቀት ይዤ ተቀመጥኩና ላገባው የምፈልገውን ሰው ፊት ነደፍኩ፡፡ ከዚያም ቁመቱንና ሌሎቹን ገጽታዎቹን ዘረዘርኩ፡፡ ጠንካራ ማንነትና ምቹ ስብዕና ያለው፣ ደግ፣ አፍቃሪና ርህሩህ፣ ተጨዋች፣ ምግባረመልካም፣ ማንነቴን የሚወድልኝ፣ እንደኔ ልጆችን የሚያፈቅርና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን የሚወድ ሰው ይሰጠኝ ዘንድ ጠየቅሁ፡፡
ለእግዚአብሔር ቀን አልቆረጥኩለትም፡፡ በዘር፣ በዜግነት ወይንም የቆዳ ቀለም ላይም ምንም ገደብ አልጣልኩ፡፡ በዓለም ላይ ከአምስት ቢሊየን በላይ ሰዎች እንደመኖራቸው - ጌታዬ የሕይወቴን አጋር የሚልክበትና እኔም የምጠብቅበት አግባብ ያለው የቆይታ ጊዜ ስድስት ወራት እንዲሆን አቀድኩ፡፡ አንድ ማስጠንቀቂያንም ጨመርኩ፡- ድንግል ማርያምን እጅግ ስለምወዳት እግዚአብሔር ከእምነቴ ተመሳሳይ የሆነ ባል ቢልክልኝ እንደሚሻል ነገርኩት፡፡ በሃይማኖት ሳቢያ በትዳሬ ምንም ዓይነት ውጥረት እንደማይኖር ማረጋገጥ እንዲሁም ባሌ እግዚአብሔርን እኔ በማመልከው መልኩ እንዲያመልክ ፈለግሁ፡፡
ምን እንደምፈልግ በትክክል ካወቅሁ በኋላ ፍላጎቴን አልመው ጀመር፡፡ ጌታ የተመኘሁትን ባርኮ እንደሚሰጠኝ፣ የልቤ መሻት እንደሚሆንልኝና የጊዜ ጉዳይ ብቻ እንደሆነ አምኜ ሁሉንም ለእርሱ ተውኩት፡፡ ሂደቱን ለማፋጠን የአባቴን ቀይና ነጭ መቁጠሪያ አወጣሁና ባሌ እንዲመጣልኝ መጸለይ ጀመርኩ፡፡ ከሦስት ወራት በኋላም መጣልኝ፡- ከእግዚአብሔር የተላከውና የተመድ የሸለመኝ አቶ ብርያን ብላክ ከአሜሪካ ድረስ ከተፍ አለ! የነገሩ መገጣጠም ደሞ ብርያን ወደ ሀገሪቱ የመጣው የዘር ማጥፋቱን በማቀድ የተሳተፉትን ለፍርድ ለማቅረብ የሚጥረውን የተመዱን ዓለም አቀፍ የሩዋንዳ ፍርድ ቤት በማቋቋሙ ሂደት ለማገዝ ሆኖ እርፍ፡፡ ብርያን ለተመድ ለብዙ ዓመታት ስለሠራ ገዳዮቹን ፍትሃዊ ቅጣት እንዲያገኙ የሚያደርገው የተልዕኮው አካል በመሆኑ ይደሰታል፡፡ በግሌ እርሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ተልዕኮ በማስፈጸም ላይ ነው፡፡
ብርያንን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመድ ግቢ ሳየው በትክክል እግዚአብሔር እንዲልክልኝ የጠየቅሁትን ሰውዬ መሰለኝ፡፡ በኋላ በአዳራሹ ሳልፈውና በዓይኖቹ የነበረውን ጥልቅ እርጋታ ሳይ እርሱ እንደሆነ እርግጠኛ ሆንኩ፡፡ ግን በእግዚአብሔር እምነቴን ስላደረግሁ ብርያንን ወደኔ እንዲያመጣው ጠበቅሁት አመጣልኛ ብርያን አብረን እንድንዝናና ጋብዞኝ ግሩም ጊዜ አሳለፍን
👍2