#ህመም_ያዘለ_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍቃዱ የሚወጣዉን ሰዉ ተመለከተዉ
ፍፁም የጀመረዉን አጋምሶ ፍቃዱ እስካሁን ስለጠፋሁበት ተመልሶ ይሆናል በማለት ለጥቂት ደቂቃ ስለተቀመጠ እግሩን እያስነከሰዉ በክራንቹ እየተመረኮዘ ሰበር ሰካ እያለ ሲወጣ
ፍቃዱ ከቅድሙ ሰዉዬ ጋር ቆሞ እያወራ ፊት ለፊት ተፋጠጡ።
ቤዛዊት በሽታዋ እያገረሸ እየተብከነከነች ብቻዋን እያወራች ወደ ፍፁም ቤት አምርታ አለመኖሩ ስታረጋግጥ አከራዩ ጋር ሄዳ
"የት ነዉ የሄደዉ?"
ለእሳቸዉ የማይጠየቅ ጥያቄ አይኖቿን እያጉረጠረጠች ጠየቀቻቸዉ
"እኔ ምን አዉቃለዉ የሚሄድበትን ነግሮኝ አይሄድ"
ሲሉ አኩዋሀኗ ያላማራቸዉ የፍፁም አከራይ መለሱላት
"እሺ እኔን የምትመስል ቁመት ብቻ የምትበልጠኝ ሴት መጥታ ነበር"
አጉረጠረጠችባቸዉ
የፍፁም ቤት አከራይ በልባቸዉ ምኗ ለካፊ ናት እያሉ
"የኔ እመቤት ማንም የመጣ ሰዉ አላየሁም አቶ ፍፁም ግን ብቻዉን ጠዋት ሲወጣ ተገናኝተን ነበር"
ይህን ሲሏት ትንሽ ተረጋጋች ከእህቴ ጋር ነዉ ስትል የነበረዉን ትታ እየከነፈች ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ደርሳ ከመግባቷ በፊት ለአፍታ ፍፁምን አሰበችዉ
"የት ሄዶ ይሆን ምን ገጠመዉ"
አይምሮዋ ግን አልተረጋጋም በቆመችበት ቦታ አንፑላንስ ድምፁን እያሰማ በአጠገቧ ሲያልፍ ጩሀቱ ስለቀፈፋት በእጆቿ ጆሮወቿን ደፍና ለደቂቃ ቆመች
መኪናዉ አልፎ ጩሀቱ እየቀነሰ ሲመጣ ተስፋ በመቁረጥ ስሜት አስፓልቱ ዳር ዝርፍጥ ብላ ተቀምጣ በአይኖቿ የፍፁምን መምጣት ትጠባበቃለች።
እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊት መጣሁ ብላ መጥፋት አሳስቧቸዉ ወደ ዉጪ ወጣ ሲሉ መንገድ ዳር ተቀምጣ አይኖቿ ሲንከራተቱ ስላዩዋት ደረታቸዉን እየደቁ እየደገፉ ወደ ቤት ለማስገባት የቤዛዊትን ሰዉነት መጎተት ጀመሩ።
"አይመጣም ቀረ..."
እያለቻቸዉ እየተሳበች እየተጎተተች ተነስታ የእማማ ስንቅነሽን ቀሚስ ጨምድዳ ይዛ እየቆመች
በታመመ አይምሮዋ የቅድሙን ቃል ደገመችላቸዉ
"አይመጣም ቀረ..."
እማማ ስንቅነሽም በዝምታ ወደ ቤት እንድትገባላቸዉ እየጎተቷት
ቅድም ያለፈዉ አንፑላንስ ተመልሶ እየጮሀ አለፈ በአሁኑ ግን ጆሮወቿን አልያዘችም በድንገት ግትር ብላ ቆማ
"ያ ዉ ያዉና መጣ"
የቀኝ እጇን የመጠቆምያ ጣት ወደ ታች ወደሚወርዱ ብዛት ያላቸዉ ሰወች ቀስራ
ፍፁም እያነከሰ በሁለት ፖሊሶች ተከቦ ከጀርባቸዉ ወሬ አድማቂ ሰዉ አጅቦት አንገቱን ደፍቶ እየተራመደ ነዉ መሬት መሬቱን እያየ ሸንከል ሸግከል እያለ ይራመዳል ፖሊሶቹ እንዲፈጥን ኮሌታዉን ይዘዉ ይጎትቱታል
ፍፁምን ካጀቡት ሰወች መሀከል
"ገድሎታል አረ አልሞተም"
እየተባባሉ ይከራከራሉ
ቤዛዊት እማማ ስንቅነሽ እጅ ላይ አይኖቿ ፍዝዝ ብለዉ በድን ሆና ቆማለች መናገር አቁማለች የምትሰማም አትመስልም የአይኖቿ ብሌኖች ብቻ በቀስታ ይንከዋለላሉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ፍፁም ፊት ለፊቱ የቆመዉን ፍቃዱን ሲያየዉ እያዘነ አይቶ እንዳላየዉ መስሎ ሊያልፈዉ ሲል ፍቃዱ ከጀርባዉ ደርሶበት
"የት ለመድረስ ነዉ የምታነክሰዉ"
ይለዋል በንቀት እግር እግሩን እያየ
ፍፁም መልስ ሳይሰጠዉ መራመዱን ሲቀጥል ፍቃዱ ደግሞ ደርሶበት እየሳቀ
"ቤዛዊትን መቼም አታገኛትም የኔ ናት አንተ ዉሻ እያዋራሁክ ደሞ የምን ንቀት ነዉ ጥለሀኝ የምትሄደዉ..."
ፍፁም መታገስ አልቻለም ክራንቹን ወደ ሰማይ አንስቶ ፍቃዱ ላይ ሳያቋርጥ ማሳረፍ ጀመረ።
ሳያስበዉ በእልህ ፍቃዱን ክፉኛ ስለመታዉ መቆም ያቃተዉ ፍቃዱ ተዝለፍልፎ ወደቀ።
💫ይቀጥላል💫
ምዕራፍ #1 በዚህ ተጠናቋል ምዕራፍ #2 በቅርቡ እንጀምራለን እስከዛው በሌሎች ጣፋጭ ድርሰቶች እንቀጥላለን እስካሁን በሄደው ድርሰት ላይ ያሎትን አስተያየት አድርሱን
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በክፍለማርያም
..ፍቃዱ የሚወጣዉን ሰዉ ተመለከተዉ
ፍፁም የጀመረዉን አጋምሶ ፍቃዱ እስካሁን ስለጠፋሁበት ተመልሶ ይሆናል በማለት ለጥቂት ደቂቃ ስለተቀመጠ እግሩን እያስነከሰዉ በክራንቹ እየተመረኮዘ ሰበር ሰካ እያለ ሲወጣ
ፍቃዱ ከቅድሙ ሰዉዬ ጋር ቆሞ እያወራ ፊት ለፊት ተፋጠጡ።
ቤዛዊት በሽታዋ እያገረሸ እየተብከነከነች ብቻዋን እያወራች ወደ ፍፁም ቤት አምርታ አለመኖሩ ስታረጋግጥ አከራዩ ጋር ሄዳ
"የት ነዉ የሄደዉ?"
ለእሳቸዉ የማይጠየቅ ጥያቄ አይኖቿን እያጉረጠረጠች ጠየቀቻቸዉ
"እኔ ምን አዉቃለዉ የሚሄድበትን ነግሮኝ አይሄድ"
ሲሉ አኩዋሀኗ ያላማራቸዉ የፍፁም አከራይ መለሱላት
"እሺ እኔን የምትመስል ቁመት ብቻ የምትበልጠኝ ሴት መጥታ ነበር"
አጉረጠረጠችባቸዉ
የፍፁም ቤት አከራይ በልባቸዉ ምኗ ለካፊ ናት እያሉ
"የኔ እመቤት ማንም የመጣ ሰዉ አላየሁም አቶ ፍፁም ግን ብቻዉን ጠዋት ሲወጣ ተገናኝተን ነበር"
ይህን ሲሏት ትንሽ ተረጋጋች ከእህቴ ጋር ነዉ ስትል የነበረዉን ትታ እየከነፈች ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።
ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ደርሳ ከመግባቷ በፊት ለአፍታ ፍፁምን አሰበችዉ
"የት ሄዶ ይሆን ምን ገጠመዉ"
አይምሮዋ ግን አልተረጋጋም በቆመችበት ቦታ አንፑላንስ ድምፁን እያሰማ በአጠገቧ ሲያልፍ ጩሀቱ ስለቀፈፋት በእጆቿ ጆሮወቿን ደፍና ለደቂቃ ቆመች
መኪናዉ አልፎ ጩሀቱ እየቀነሰ ሲመጣ ተስፋ በመቁረጥ ስሜት አስፓልቱ ዳር ዝርፍጥ ብላ ተቀምጣ በአይኖቿ የፍፁምን መምጣት ትጠባበቃለች።
እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊት መጣሁ ብላ መጥፋት አሳስቧቸዉ ወደ ዉጪ ወጣ ሲሉ መንገድ ዳር ተቀምጣ አይኖቿ ሲንከራተቱ ስላዩዋት ደረታቸዉን እየደቁ እየደገፉ ወደ ቤት ለማስገባት የቤዛዊትን ሰዉነት መጎተት ጀመሩ።
"አይመጣም ቀረ..."
እያለቻቸዉ እየተሳበች እየተጎተተች ተነስታ የእማማ ስንቅነሽን ቀሚስ ጨምድዳ ይዛ እየቆመች
በታመመ አይምሮዋ የቅድሙን ቃል ደገመችላቸዉ
"አይመጣም ቀረ..."
እማማ ስንቅነሽም በዝምታ ወደ ቤት እንድትገባላቸዉ እየጎተቷት
ቅድም ያለፈዉ አንፑላንስ ተመልሶ እየጮሀ አለፈ በአሁኑ ግን ጆሮወቿን አልያዘችም በድንገት ግትር ብላ ቆማ
"ያ ዉ ያዉና መጣ"
የቀኝ እጇን የመጠቆምያ ጣት ወደ ታች ወደሚወርዱ ብዛት ያላቸዉ ሰወች ቀስራ
ፍፁም እያነከሰ በሁለት ፖሊሶች ተከቦ ከጀርባቸዉ ወሬ አድማቂ ሰዉ አጅቦት አንገቱን ደፍቶ እየተራመደ ነዉ መሬት መሬቱን እያየ ሸንከል ሸግከል እያለ ይራመዳል ፖሊሶቹ እንዲፈጥን ኮሌታዉን ይዘዉ ይጎትቱታል
ፍፁምን ካጀቡት ሰወች መሀከል
"ገድሎታል አረ አልሞተም"
እየተባባሉ ይከራከራሉ
ቤዛዊት እማማ ስንቅነሽ እጅ ላይ አይኖቿ ፍዝዝ ብለዉ በድን ሆና ቆማለች መናገር አቁማለች የምትሰማም አትመስልም የአይኖቿ ብሌኖች ብቻ በቀስታ ይንከዋለላሉ።
(ከደቂቃወች በፊት)
ፍፁም ፊት ለፊቱ የቆመዉን ፍቃዱን ሲያየዉ እያዘነ አይቶ እንዳላየዉ መስሎ ሊያልፈዉ ሲል ፍቃዱ ከጀርባዉ ደርሶበት
"የት ለመድረስ ነዉ የምታነክሰዉ"
ይለዋል በንቀት እግር እግሩን እያየ
ፍፁም መልስ ሳይሰጠዉ መራመዱን ሲቀጥል ፍቃዱ ደግሞ ደርሶበት እየሳቀ
"ቤዛዊትን መቼም አታገኛትም የኔ ናት አንተ ዉሻ እያዋራሁክ ደሞ የምን ንቀት ነዉ ጥለሀኝ የምትሄደዉ..."
ፍፁም መታገስ አልቻለም ክራንቹን ወደ ሰማይ አንስቶ ፍቃዱ ላይ ሳያቋርጥ ማሳረፍ ጀመረ።
ሳያስበዉ በእልህ ፍቃዱን ክፉኛ ስለመታዉ መቆም ያቃተዉ ፍቃዱ ተዝለፍልፎ ወደቀ።
💫ይቀጥላል💫
ምዕራፍ #1 በዚህ ተጠናቋል ምዕራፍ #2 በቅርቡ እንጀምራለን እስከዛው በሌሎች ጣፋጭ ድርሰቶች እንቀጥላለን እስካሁን በሄደው ድርሰት ላይ ያሎትን አስተያየት አድርሱን
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...“ እንዲያው ምን ምን ይላት ይሆን?እኔ እሱ ለሴት ልጅ የሚያወራውን ነገር ለመስማት እጓጓለሁ " ግን አንተ ባል
ከው ዐይነት አገጣጥሞኝ አያውቅም ። ”
“አጅሬ ምኑ ሞኝ ነው ላንተ የሚታየው ?!እሷን ሲያገኛት ቦታው ጭር የሚልበትን ጊዜ ጠብቆ ነው ።
“ ወይ ጉድ ! መቼም ፍቅር የማያሸንፈው ልብ የለም ”አለ እስክንድር በልቡ ። ስለ ድብርት የበለጠ ለማወቅ ጓጉቶ ነበር ። ሆኖም ጨዋታው በተዘዋዋሪም ቢሆን አንዳንድ የአቤልን ድርጊቶች እንደሚንካ ስለ ገመተ አርዕስቱን ለመለወጥ ፈለገ ሳምሶንም ይህንን ሁሉ ልብ ሳይል እንደ መጣለት ነበር የሚጫወተው ። እስክንድር ግን የአቤል ስሜት
እየተለዋወጠ እንደ መጣ በሥርቆት ከገጽታው ላይ አንብቦአል ድብርት የሴት ጓደኛውን ለማግኘት ጭር ያለ ጊዜ
መጠበቁ የአቤልን ስሜት ክፉኛ ነክቶታል እሱም ትዕግሥትን ለማየት የሚጠቀምባቸውን ጊዜያቶች ያውቃል ።
ስማኝ ላምሶን ! ግን ለምንድነው አንተ ብዙ ጊዜ ድብርትን የምትለክፈው ? ” በማለት እስክንድር አርዕስቱን አሸጋገረው
“ ለተንኮል አይደለም ። ግን የሚነፋነፍ ሰው መልከፍ እንዲሁ ደስ ይለኛል ። እንዴት ብዬ ላስረዳህ ? ለምሳሌ
ቀርቦ መናከስ የማይደፍር ውሻ በሩቁ እያፈገፈገ ሲጮህብህ እልሁን ለማስጨራረስ በዱላ እንደምትተናኮለው ዐይነት ነው ። ብቻ እንዲሁ ስለክፈው ደስ ይለኛል እንጂ ለድብርት መጥፎ አመለካከት የለኝም ለየት ያለ ተፈጥሮ ስላለው ያስገርመኛል ” አለና አሳላፊዋን ለመጥራት ጠረጴዛውን ጠበጠበ።
“ አቤት ! ምን ልታዘዝ? ” እያለች አንገቷ በንቅሳት የተዥጎረጎረ ሴት ከፊታቸው መጥታ ቆመች ።
“ ቢራ ድገሚን ሦስት ቢራ ! ” አላት ሳምሶን በዚያው ቁጡ ድምፁ
“ እኔ ይብቃኝ ! ” አለ አቤል "
“ አትቀልድ እባክህ ። አንቺ እኔ የማዝሽን አምጪ!” አለና ሳምሶን አሳላፊዋ ላይ ጮኸባት ።
"ጥርስሽን እንዳያወልቅ ” አለና እስክንድር በልቡ ሳቀ ።
“ እኔኮ ያንተም ተፈጥሮ ያስገርመኛል ” አለው እስክንድር ሳምሶንን
“ እንዴት ?”
“ አሁን ሚስተር ሆርስ ከአቤል ጋር ከታረቀ በኋላ ለምን ትዝትበታለህ ?”
“ አዎ ! የማታውቀው ነገር አለ እስክንድር እየዛትክ የምትተው ከሆነ ዛቻው ሲደጋገም ሰው ይንቅሃል ።ወንድ ከሆንክ አንዴ ማቅመስ አለብህ ። እንዲያውም አንተን ብዬ ነው እንጂ እሱን ልጅ አንድቀን ብሰብረው ደስይለኛል ። ከፈለገ የገዛ ጥርሱን ከመሬት አሰለቅመዋለሁ ።
“ጡንቻህን ፈትነኝ እያለ ያስቸግሃል መሰለኝ” አለና እስክንድር እየሣቀ ከእሱ መልስ ሳይጠብቅ ፡ “ ብቻ ያለንበትንም ጊዜ አትዘንጋ : ሀያኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነን ” አለው ።
“ እና ? ” የብሽቀት ድምፅ ነበር ።
“ እናማ ስፖርተኝነትህን እወድልሃለሁ ። ይህችን በጡንቻ መመካትህን ግን ...
“ እንግዲህ አትልከፈኝ ፡ ልጠጣበት ! ” አለና ቢራውን ተጎነጨ
ሳምሶን ሌላ ሰው እንዲህ ቢናገረውም ካልተደባደበ በዋዛ እይላቀቁም ነበር ። ለእስክንድር ያለው ክብር ግን ብዙ ዓመት ከቆየ የልጅነት የአስተሳሰብ ተጽዕኖ የመጣ ነው ። የሠፈር ልጆች እንደ መሆናቸው መጠን ሳምሶን ስለ እስክንድር ብዙ ነገር ያውቃል ። እሱ ገና ልጅነቱን ሳይጨርስ እስክንድር በሠፈራቸው ውስጥ ስመ ጥር ጎረምሳ
ነበር ። እንዲህ እንዳሁኑ ከመስከኑ በፊት እናቱ በእስክንድር ያላዩት አበሳ የለም ። ከለውጡ በፊት ጸብ አሽትቶ ነበር
የሚፈልገው ። እስር ቤትን ቤቱ አድርጎት ነበር ። አንዴ ጸበኞቹ በቡድን ሆነው ከደበደቡት በኋላ ሆዱ ላይ በጩቤ
ወግተውት ለጥቂት ነው ከምት የተረፈው ከለውጡ በኋላ ደግሞ በወቅቱ በተፈጠሩት የፖለቲካ ድርጅቶች ሳቢያ
ያልቀመሰው፡ አበሳ የለም ። ችኩል ነበር ። ሰው አይገራውም ፣ ያየሁት አይለፈኝ የሚል ስሜት ያሸንፈዋል ።
የጀብደኝነት ስሜት ያጠቃዋል ። ትኩስ ኃያልነቱ፡ መንፈሱን ያቅበጠብጠዋል ። አሁን ግን በዕድሜም በብስለትም ሰክኖ
እንኳን ለራሰ ሌሎችንም ይመክራል ። ከአፍላነት ቅብጥብጥነት ጊዜው ይዞ የመጣውና አሁንም ያልተወው ነገር ቢኖር
የሲጋራ ሱስ ብቻ ነው። ይህ ሁሉ ሁኔታ በሳምሶን ላይ የሚኖረው ተጽእኖ ቀላል አይደለም። በፀጉሩ ኪንኪነት እየለከፈው ከእስክንድር ጋር መቃለድ የጀመረው እንኳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው።
አቤል እባክህ ተጫወት ይሄንን ተወው
አለ ሳምሶን እስክንድርን በመንቀፍ አይነት
“ እየሰማኋችሁ “ኮ ነው ? ” አለ አቤል በጨዋታቸው ውስጥ የቆየ ለመምሰል ጥርሱን በውሸት ብልጭ አደረገ።
ሐሳቡ በከፌል ወደ እነ ትእግስት ዘምቶ ነበረ። ፈተና ከጨረሰች በኋሳ ወዴት ትሔድ ይሆን ? አርፎ መተኛት ወይስ
ዙረት መውጣት ? እያለ ሲያሰላስል ነው የቆየው።ሁለተኛውን ጠርሙስ ቢራ ግማሽ አድርሶታል ። ከቻቻታው ጋር
ቢራው ሞቅ አድርጎት ውስጥ ውስጡን እየሰከረ መምጣቱ ይሰማው ነበር። የመጠጣት ልምድ ስለሌለው ጭንቅላቱ ቶሎ መረታት ጀምሯል ። ድፍረትም ተሰማው ማንንም ያለመፍራት ሃይነት ስሜት !
“ ለምን ሙዚቃውን አይቀይሩልንም ? ” ሲል ድምፁን አሰማ ። የእንግሊዝኛ ሙዚቃ ነበር አዳራሹን የሚነቀንቀው፤“ ማስቀየር እንችላለን ። የማን ክር ይደረግ ? ” አሉ እስክንድርና ሳምሶን በአንድ ድምፅ አቤል ከዝምታ ወደ
ተሳትፎ መምጣቱ ደስ አሰኝቶአቸው ነበር
•የ... የመልካሙ ተበጀ ክር ቢሆን
ይሻላል” አለ አቤል በተሰባበረ ድምፅ
እስክንድርም ሆነ ሳምሶን በፍጥነት የጠረጠሩት ነገር አልነበረም ። አሳላፊዋን ጠርተው ክሩ እንዲቀየር አዘዟዋት።
ባለቤትየዋ እሷ የመረጠችው ዘፈን ካልሆን እሺ አትልም ግን ልሞክርላችሁ ” አለች አሳላፊዋ ።
“ ንገሪያት ! ለምን እሺ አትልም ? ” አለና ሳምሶን አፈጠጠበት እሷ ዘፈኑን ልታዝዝ ስትሔድ አቤል ቀድሞ በልቡ
ያንጐራጉር ጀመር።
አረ መላ ምቱ ወዳጅ ዘመዶቼ
ዐይናፋር ሆኛለሁ ፡ ዐይናፋር አይቼ
ሰሳምታ አልሰጠኋት አላነጋገርኳት
በዐይን ብቻ እያየሁ አንድ ዓመት ወደድኳት።
ልቡ ይህን እያዜመ፥ ጆሮው የሚሰማው ግን ሌላ ሙዚቃ ነበር ቢጠብቅ ፥ ቢጠብቅ የተለወጠ ነገር የለም ጥቂት
ቆይታ አሳላፊዋ ተመልሳ መጣች።
የመልካሙ ክር የለም ብላለች ባለቤትየዋ ! ”
አቤል በሽቆ “ ገደል ግቢ በያት ! ” ከማለቱ ዐይኑ እንባ አቀረረ ። የሰው ስሜት የማይጠበቅበት ዓለም ! ባለቡና ቤቶች ፍቅረኛውን የሚያስታውስበትን ዘፈን አይከፍቱለትም "መምህራን ትምህርት ምን ያህል እንዳስጠላው አይረዱለትም ። ወላጆቹ ልጃቸው ከድህነት ቀንበር እንዲያላቅቃቸው
ይመኛሉ እንጂ እሱ ያለበትን ችግር አያውቁለትም ። ጓደኞቹ ብቸኝነቱን አይፈቅዱለትም ።
“ እሷ ከሙዚቃዋ ጋር ገደል ትግባ ! አንቺ ቢራ ድግሚን ” አላት ሳምሶን በሽቆ ።
“ኧረ ይብቃን ! ሰዓቱም መሽቷል የካምፓስ ፖሊሶች አያስገቡንም ” አለ እንክንርድ ኪሱን እየዳበሰ ።
አምጪልን እባክሽ እንጠጣው ዛሬ ካምፓስ ማን ይገባል? ” አለ ሳምሶን በሞቅታ ስሜት ።
“በይ እንግዲያው አንቺንም እንጋብዝሽ የምትጠጪውን ነገር ይዘሽ ነይ ” አላትና እስክንድር ፡ ወደ ሳምሶን ዘወር ብሎ ፥ “ ከጠጣን አይቀር መሐላችን አንዲት አንስታይ ስትኖር ይሻላል” አለው ። ከሳምሶን ሁኔታ ገንዘብ እንደያዘ
ገምቶ ነበር "
እቤል ምንም አስተያየት አልሰጠም ። የያዘውን ቢራም አልጨረሰም ። ከዚያ በላይ መጠጣት አልፈለገም ። ሆኖም
አልተከላከለም ። ሕይወትን የመሰልቸት ዐይነት ነበር የሚሰማው ። ለምንም ነገር ያለመጨነቅ ። ስካር ማለት ይሄ ይሆን እንዴ?
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...“ እንዲያው ምን ምን ይላት ይሆን?እኔ እሱ ለሴት ልጅ የሚያወራውን ነገር ለመስማት እጓጓለሁ " ግን አንተ ባል
ከው ዐይነት አገጣጥሞኝ አያውቅም ። ”
“አጅሬ ምኑ ሞኝ ነው ላንተ የሚታየው ?!እሷን ሲያገኛት ቦታው ጭር የሚልበትን ጊዜ ጠብቆ ነው ።
“ ወይ ጉድ ! መቼም ፍቅር የማያሸንፈው ልብ የለም ”አለ እስክንድር በልቡ ። ስለ ድብርት የበለጠ ለማወቅ ጓጉቶ ነበር ። ሆኖም ጨዋታው በተዘዋዋሪም ቢሆን አንዳንድ የአቤልን ድርጊቶች እንደሚንካ ስለ ገመተ አርዕስቱን ለመለወጥ ፈለገ ሳምሶንም ይህንን ሁሉ ልብ ሳይል እንደ መጣለት ነበር የሚጫወተው ። እስክንድር ግን የአቤል ስሜት
እየተለዋወጠ እንደ መጣ በሥርቆት ከገጽታው ላይ አንብቦአል ድብርት የሴት ጓደኛውን ለማግኘት ጭር ያለ ጊዜ
መጠበቁ የአቤልን ስሜት ክፉኛ ነክቶታል እሱም ትዕግሥትን ለማየት የሚጠቀምባቸውን ጊዜያቶች ያውቃል ።
ስማኝ ላምሶን ! ግን ለምንድነው አንተ ብዙ ጊዜ ድብርትን የምትለክፈው ? ” በማለት እስክንድር አርዕስቱን አሸጋገረው
“ ለተንኮል አይደለም ። ግን የሚነፋነፍ ሰው መልከፍ እንዲሁ ደስ ይለኛል ። እንዴት ብዬ ላስረዳህ ? ለምሳሌ
ቀርቦ መናከስ የማይደፍር ውሻ በሩቁ እያፈገፈገ ሲጮህብህ እልሁን ለማስጨራረስ በዱላ እንደምትተናኮለው ዐይነት ነው ። ብቻ እንዲሁ ስለክፈው ደስ ይለኛል እንጂ ለድብርት መጥፎ አመለካከት የለኝም ለየት ያለ ተፈጥሮ ስላለው ያስገርመኛል ” አለና አሳላፊዋን ለመጥራት ጠረጴዛውን ጠበጠበ።
“ አቤት ! ምን ልታዘዝ? ” እያለች አንገቷ በንቅሳት የተዥጎረጎረ ሴት ከፊታቸው መጥታ ቆመች ።
“ ቢራ ድገሚን ሦስት ቢራ ! ” አላት ሳምሶን በዚያው ቁጡ ድምፁ
“ እኔ ይብቃኝ ! ” አለ አቤል "
“ አትቀልድ እባክህ ። አንቺ እኔ የማዝሽን አምጪ!” አለና ሳምሶን አሳላፊዋ ላይ ጮኸባት ።
"ጥርስሽን እንዳያወልቅ ” አለና እስክንድር በልቡ ሳቀ ።
“ እኔኮ ያንተም ተፈጥሮ ያስገርመኛል ” አለው እስክንድር ሳምሶንን
“ እንዴት ?”
“ አሁን ሚስተር ሆርስ ከአቤል ጋር ከታረቀ በኋላ ለምን ትዝትበታለህ ?”
“ አዎ ! የማታውቀው ነገር አለ እስክንድር እየዛትክ የምትተው ከሆነ ዛቻው ሲደጋገም ሰው ይንቅሃል ።ወንድ ከሆንክ አንዴ ማቅመስ አለብህ ። እንዲያውም አንተን ብዬ ነው እንጂ እሱን ልጅ አንድቀን ብሰብረው ደስይለኛል ። ከፈለገ የገዛ ጥርሱን ከመሬት አሰለቅመዋለሁ ።
“ጡንቻህን ፈትነኝ እያለ ያስቸግሃል መሰለኝ” አለና እስክንድር እየሣቀ ከእሱ መልስ ሳይጠብቅ ፡ “ ብቻ ያለንበትንም ጊዜ አትዘንጋ : ሀያኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነን ” አለው ።
“ እና ? ” የብሽቀት ድምፅ ነበር ።
“ እናማ ስፖርተኝነትህን እወድልሃለሁ ። ይህችን በጡንቻ መመካትህን ግን ...
“ እንግዲህ አትልከፈኝ ፡ ልጠጣበት ! ” አለና ቢራውን ተጎነጨ
ሳምሶን ሌላ ሰው እንዲህ ቢናገረውም ካልተደባደበ በዋዛ እይላቀቁም ነበር ። ለእስክንድር ያለው ክብር ግን ብዙ ዓመት ከቆየ የልጅነት የአስተሳሰብ ተጽዕኖ የመጣ ነው ። የሠፈር ልጆች እንደ መሆናቸው መጠን ሳምሶን ስለ እስክንድር ብዙ ነገር ያውቃል ። እሱ ገና ልጅነቱን ሳይጨርስ እስክንድር በሠፈራቸው ውስጥ ስመ ጥር ጎረምሳ
ነበር ። እንዲህ እንዳሁኑ ከመስከኑ በፊት እናቱ በእስክንድር ያላዩት አበሳ የለም ። ከለውጡ በፊት ጸብ አሽትቶ ነበር
የሚፈልገው ። እስር ቤትን ቤቱ አድርጎት ነበር ። አንዴ ጸበኞቹ በቡድን ሆነው ከደበደቡት በኋላ ሆዱ ላይ በጩቤ
ወግተውት ለጥቂት ነው ከምት የተረፈው ከለውጡ በኋላ ደግሞ በወቅቱ በተፈጠሩት የፖለቲካ ድርጅቶች ሳቢያ
ያልቀመሰው፡ አበሳ የለም ። ችኩል ነበር ። ሰው አይገራውም ፣ ያየሁት አይለፈኝ የሚል ስሜት ያሸንፈዋል ።
የጀብደኝነት ስሜት ያጠቃዋል ። ትኩስ ኃያልነቱ፡ መንፈሱን ያቅበጠብጠዋል ። አሁን ግን በዕድሜም በብስለትም ሰክኖ
እንኳን ለራሰ ሌሎችንም ይመክራል ። ከአፍላነት ቅብጥብጥነት ጊዜው ይዞ የመጣውና አሁንም ያልተወው ነገር ቢኖር
የሲጋራ ሱስ ብቻ ነው። ይህ ሁሉ ሁኔታ በሳምሶን ላይ የሚኖረው ተጽእኖ ቀላል አይደለም። በፀጉሩ ኪንኪነት እየለከፈው ከእስክንድር ጋር መቃለድ የጀመረው እንኳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ነው።
አቤል እባክህ ተጫወት ይሄንን ተወው
አለ ሳምሶን እስክንድርን በመንቀፍ አይነት
“ እየሰማኋችሁ “ኮ ነው ? ” አለ አቤል በጨዋታቸው ውስጥ የቆየ ለመምሰል ጥርሱን በውሸት ብልጭ አደረገ።
ሐሳቡ በከፌል ወደ እነ ትእግስት ዘምቶ ነበረ። ፈተና ከጨረሰች በኋሳ ወዴት ትሔድ ይሆን ? አርፎ መተኛት ወይስ
ዙረት መውጣት ? እያለ ሲያሰላስል ነው የቆየው።ሁለተኛውን ጠርሙስ ቢራ ግማሽ አድርሶታል ። ከቻቻታው ጋር
ቢራው ሞቅ አድርጎት ውስጥ ውስጡን እየሰከረ መምጣቱ ይሰማው ነበር። የመጠጣት ልምድ ስለሌለው ጭንቅላቱ ቶሎ መረታት ጀምሯል ። ድፍረትም ተሰማው ማንንም ያለመፍራት ሃይነት ስሜት !
“ ለምን ሙዚቃውን አይቀይሩልንም ? ” ሲል ድምፁን አሰማ ። የእንግሊዝኛ ሙዚቃ ነበር አዳራሹን የሚነቀንቀው፤“ ማስቀየር እንችላለን ። የማን ክር ይደረግ ? ” አሉ እስክንድርና ሳምሶን በአንድ ድምፅ አቤል ከዝምታ ወደ
ተሳትፎ መምጣቱ ደስ አሰኝቶአቸው ነበር
•የ... የመልካሙ ተበጀ ክር ቢሆን
ይሻላል” አለ አቤል በተሰባበረ ድምፅ
እስክንድርም ሆነ ሳምሶን በፍጥነት የጠረጠሩት ነገር አልነበረም ። አሳላፊዋን ጠርተው ክሩ እንዲቀየር አዘዟዋት።
ባለቤትየዋ እሷ የመረጠችው ዘፈን ካልሆን እሺ አትልም ግን ልሞክርላችሁ ” አለች አሳላፊዋ ።
“ ንገሪያት ! ለምን እሺ አትልም ? ” አለና ሳምሶን አፈጠጠበት እሷ ዘፈኑን ልታዝዝ ስትሔድ አቤል ቀድሞ በልቡ
ያንጐራጉር ጀመር።
አረ መላ ምቱ ወዳጅ ዘመዶቼ
ዐይናፋር ሆኛለሁ ፡ ዐይናፋር አይቼ
ሰሳምታ አልሰጠኋት አላነጋገርኳት
በዐይን ብቻ እያየሁ አንድ ዓመት ወደድኳት።
ልቡ ይህን እያዜመ፥ ጆሮው የሚሰማው ግን ሌላ ሙዚቃ ነበር ቢጠብቅ ፥ ቢጠብቅ የተለወጠ ነገር የለም ጥቂት
ቆይታ አሳላፊዋ ተመልሳ መጣች።
የመልካሙ ክር የለም ብላለች ባለቤትየዋ ! ”
አቤል በሽቆ “ ገደል ግቢ በያት ! ” ከማለቱ ዐይኑ እንባ አቀረረ ። የሰው ስሜት የማይጠበቅበት ዓለም ! ባለቡና ቤቶች ፍቅረኛውን የሚያስታውስበትን ዘፈን አይከፍቱለትም "መምህራን ትምህርት ምን ያህል እንዳስጠላው አይረዱለትም ። ወላጆቹ ልጃቸው ከድህነት ቀንበር እንዲያላቅቃቸው
ይመኛሉ እንጂ እሱ ያለበትን ችግር አያውቁለትም ። ጓደኞቹ ብቸኝነቱን አይፈቅዱለትም ።
“ እሷ ከሙዚቃዋ ጋር ገደል ትግባ ! አንቺ ቢራ ድግሚን ” አላት ሳምሶን በሽቆ ።
“ኧረ ይብቃን ! ሰዓቱም መሽቷል የካምፓስ ፖሊሶች አያስገቡንም ” አለ እንክንርድ ኪሱን እየዳበሰ ።
አምጪልን እባክሽ እንጠጣው ዛሬ ካምፓስ ማን ይገባል? ” አለ ሳምሶን በሞቅታ ስሜት ።
“በይ እንግዲያው አንቺንም እንጋብዝሽ የምትጠጪውን ነገር ይዘሽ ነይ ” አላትና እስክንድር ፡ ወደ ሳምሶን ዘወር ብሎ ፥ “ ከጠጣን አይቀር መሐላችን አንዲት አንስታይ ስትኖር ይሻላል” አለው ። ከሳምሶን ሁኔታ ገንዘብ እንደያዘ
ገምቶ ነበር "
እቤል ምንም አስተያየት አልሰጠም ። የያዘውን ቢራም አልጨረሰም ። ከዚያ በላይ መጠጣት አልፈለገም ። ሆኖም
አልተከላከለም ። ሕይወትን የመሰልቸት ዐይነት ነበር የሚሰማው ። ለምንም ነገር ያለመጨነቅ ። ስካር ማለት ይሄ ይሆን እንዴ?
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ።
ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች። ናፍቆቷን ሙሉውን ሌሊት አቅፋት በመተኛት ተወጣች፡፡
አሁን ሁሉንም ጣጣዋን ጨርሳለች፡፡ ዕቅዷን ልትፈጽም ሰዓቱ እየደረሰ ነው፡፡ በሌሊት ተነስታ ልብሷን ለባብሳ ጨረሰችና፣ ከፔርሙስ ትንሽ አጥሚት ቀድታ ካጠጣቻት በኋላ፤ “ወደ ቤት ልሂድ እማ!” ብላ ለመሄደ ተነሳች፡፡
ደግማ፤ ደጋግማ፤ ጉንጮቿን አገላብጣ ሳመቻትና፤ ወጣች፡፡ስትወጣ መንፈሷ ሁሉ ጠንካራ ነበር፡፡ ፍርሀት ጓዙን ጠቅልሎ ነው የሄደው፡፡ ቤት ደርሳ ያንን ትናንትና በፍቅር ስታሽሞነሙነው የዋለችውን የአባቷን ቅርስ ሸፋፍና፤ በቦርሳዋ ይዛ፤ ወደ መርካቶ ገሰገሰች፡፡
እዚያ እፍልሚያው ቦታ ስትደርስ ከታክሲ ወረደችና ራቅ ብላ ዓይኖቿን በሱቁ ላይ ተክላ ትጠባበቅ ጀመር፡፡
ልቧ ድው! ድው፤ ይላል፡፡ እልህና ሲቃ ይተናነቋታል፡፡ እንዷ ደቂቃ አቤት ርዝመቷ! አውሬው ወጥመዱ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ በንቃት መጠባበቋን ቀጠለች፡፡
አንዳንድ ሱቆች መከፈት ጀምረዋል፡፡ እምብዛም ሰው አይታይም፡፡ መርካቶ ትንሽ ሞቅ ሲል እንደዚያ እንደማይተራመስ ሁሉ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያስገርም ነው፡፡
ነጠላዋን ተሸፋፍና፣ መንገደኛ መስላ፧ አንድ ጥግ ላይ ተቀመጠችና፤ ግዳይዋን መጠባበቁን ተያያዘችው፡፡ በእርግጥም ስለቸኮለች ነው መሰል በጣም ቀድማ ነበር የመጣችው፡፡
ገንዘብ በገፍ እየገባለት የመጣው ጎረምሳ በንግዱ ላይ ትኩረቱን እየጣለ ሄዶ ነበር፡፡ አበራን ወደዚያ ካባረረ በኋላ ትርፉን ለግሉ ማግበስበስ ጀምሯል።
ገንዘብ ሲቀምሱት ይጣፍጣል፡፡ በላይ በላዩ ያስመኛል። እህል ሲጠግቡት ያስገሳል፡፡ሲበዛም ያስጠላል፡፡ ገንዘብ የሚጠግብ ሆድ ግን የለም፡፡ ግሳትም የለው፡፡ በላይ በላዩ ጨምሩልኝ፣ ጨምሩልኝ፣ የሚያሰኝ፣ እየበሉት የሚርብ ነገር ቢኖር ገንዘብ ነው፡፡
እንደሻው የራሱ የሆነውን፤ እንደፈለገው የሚያዝበትን ገንዘብ ሲያገኝ፤ እንደጠላት ገንዘብ ማውደም ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ ሱቁን በማደራጀት ሀብታም መሆን ስለፈለገ፣ ቆጣቢና ትጉህ ሠራተኛ ሆኗል።
ዛሬ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ገበያ ሊሻማ መጣና የሱቁን በር ከፈተ፡፡ ሙሉ ጂንስ ለብሷል፡፡ ከላይ ጥቁር ክብ ባርኔጣ አድርጓል፡፡
አንገቱ ላይ አጠር ያለች ወፍራም ሻርፕ ጠምጥሞ ነበር፡፡
የሱቁን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ መዝለቁን ስታይ ትህትና ተዘጋጀች፡፡ እሷም ጂንስ ሱሪ ነው የለበሰችው፡፡
ቀስ ብላ ቀኝ እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰደደችና፣ ማጥበቂያውን አላላች፡፡ ሽጉጡ ላግዳጁ ዝግጁ ሆነ፡፡ አሁንም ቀስ ብላ ጨበጠቸው፡፡ እጇ የተንቀጠቀጠ መሰላት፡፡
“አይዞሽ ትህትና ጠንከር በይ” አለች ለራሷ፡፡ “የመጨረሻው ሰዓት የድል ሰዓት ደርሷል፡፡ የመጨረሻውን የድል ሰዓት ባትወጪው አበቃልሽ!” አለችና ራሷን አደፋፈረች፡፡
ይህ የመጨረሻው መክሸፍ የሌለበት እርምጃ ነው፡፡ በእውነትም ጠንከር አለች፡፡ ልቧ በትክክል መምታት ጀመረ፡፡ ሰውነቷ መራራ ደም ሲረጭ ተሰማት፡፡ የቀድሞ ባህሪዋ ከውስጧ ጥርግርግ ብሎ ወጣና፤ አዲስ የቆራጥነት፣ የደፋርነትና፤ የጭካኔ ባህሪይ ተላበሰች፡፡
“አምላኬ በደሌን አንተ ይቅር በለኝ፡፡ ነፍሴን ተቀበላት!” አለችና የሽጉጡን ምላጭ እንደያዘች እየተንደረደረች ወደ ሱቁ ሩጫዋን ቀጠለች፡፡
ሱቁ በር ላይ ስትደርስ እንደሻው በሚያየው ነገር ተደናግጦ፣ ዐይኖቹ ተበልጥጠው፣ አፉ ተከፍቶ እንደቀረ ትንፋሽ ከማውጣቱ በፊት
ሽጉጡን ላጥ አድርጋ አወጣችው፡፡
ንግግር የለ፣ ግርግር የለ፣ ፋታ ሳትሰጠው በቀጥታ እርምጃውን ወሰደች፡፡
ዷ! ዷ! ዷ! ዷ! አምስት የቆጠረች መሰላት፡፡ አራንቱን ጥይቶች ካንጣጣችበት በኋላ፣ ተንገዳግዶ መውደቁን ስታረጋግጥ፧ ሽጉጡን
ወደራሷ አዙራ አፍዋ ውስጥ አስገባቸው፡፡
ሰው መሯሯጥ ጀመረ፡፡ ለሚተራመሰው ሰው ቦታ ሳትሰጥ፤
እርምጃዋን በራሷ ላይ ወሰደች፡፡ ምላጩን ሳበቸው፡፡ ዷ! ዷ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ የተባዘተ ጥጥ በመሰለው ደመና ተዥጐርጉሯል።
ጨረሯን የፈነጠቀችው ፀሐይ ያንን የደመና ቁልል እየናደችው ስትመጣ፤
ሰዓሊው በሸራ ላይ በብሩሹ የፈነጠቀው ንድፍ እየመሰለ ሄደ፡፡ ከዚያም ሙሉ ለሙሉ ደመናው ተገፈፈና፤ ጥርት ያለ ሰማይ ታየ፡፡
የሰው ልጅ የውስጥ ስሜቱ ሲጐዳ፣ ሲከፋው፣ ሲጨንቀው፤ ልክ ሰማዩ በደመና እንደሚያኮርፈው ሁሉ፤ ይህንን መጥፎ የውስጥ ስሜቱን በጨፈገገ ገጽታው ይገልጸዋል፡፡ በሆነ ባልሆነው ሆደ ባሻነት ያጠቃዋል፡፡
እነሆ ልቡ ከአምስት ዓመታት በላይ ከፍቅር ተገልሎ የቆየው ሻምበል ብሩክ ትህትናን ካገኘበት እለት ጀምሮ መንፈሱ ታድሶ!
የወደፊት የትዳር ህይወቱን በቅርብ ርቀት አሻግሮ መመልከት ሲጀምር፤ በእንጭጩ ተቀጨ፡፡
ትህትና ፍቅሯን ብቻ ሳይሆን፤ ያንን ደስተኛነቱን ጭምር በልቡ ውስጥ ገድላበት ነው የሄደችው፡፡
ድምጿን ለመስማት ይፈልጋል፣ ወዲያውኑ ደግሞ ከነመፈጠሯ እንዲረሳት ይመኛል፡፡ ትናፍቀዋለች፤ የሠራችው በደል ፊቱ ላይ ድቅን
ይልበታል፡፡ በቅናት ይቃጠላል፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ ብሩኬ.... ብሩኬ....
ብሩኬ.... የሚለው ያ ለስላሳ ድምጿ፣ ያ ለስላሳ ሰውነቷ ያ ለስላሳ ባህሪዋ፤ ይታወሰዋል፡፡
በፊት የነበረችው ትህትና እንዴት የምትወደድ ልጅ ነበረች? ለምን ፈጣሪ አሳይቶ ነሳው? ምነው እሱ ለፍቅር አልታደለ? ሁል ጊዜ መጨነቅ?
“ምነው የዚያን ዕለት ባልተገናኘን ኖሮ” የሚል ሃሣብ መጣበት፡፡ ሆኖም በመገናኘታቸው አንድ መልካም ሥራ መስራቱ ያስደስተዋል፡፡
አጋር ያልነበራት እናቷን መርዳት መቻሉ እርካታን ይሰጠዋል።
ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም፡፡ እንዲሉ፣ እሷ ትበድለው እንጂ፤ እሱ ከበደል ይልቅ መልካም ሥራን የሠራ ተበዳይ መሆኑ ሲታወሰው፤ “ይሁን እስቲ ሁሉ ነገር ከፈጣሪ ይገኛል” ይልና
ይጽናናል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ የሰሞኑ ሁኔታው የተለየ ነበር፡፡ ናፍቆቷ ነፍሱን ሊያወጣው ደርሷል፡፡
በውስጡ ፍቅርና ጥላቻ ነግሰውበታል፡፡ እንዳይጠላት ይወዳታል፣ እንዳይወዳት ደግሞ የሠራችው ሥራ...እንዳንድ ጊዜ ያ አለቃቀሷ፤ እዚያ እላዩ ላይ ተጠምጥማ እየተንሰቀሰቀች የተናገረችው ንግግር፣ ትዝ ይለውና፤ “ምን ነበረበት ይቅር ብላት ኖሮ? ግብዝ ነኝ” በማለት እራሱን
ይኮንናል፡፡ ወዲያው ደግሞ የሻክረና ጥርጣሬ የገባው ልብ ተመልሶ ልብ
ላይሆን፡፡ የነቃ ብርሌ ተመልሶ ዕቃ ላይሆን፣ አጉል ሙጥኝ አለማለቱን
ይወደውና..
እንኳንም በጊዜ አቋረጥን” የሚል ስሜት ይሰማዋል፡፡በጠዋቱ መ/ቤቱ እንደደረሰ ወደ ቢሮ ከመግባቱ በፊት ጫማውን
ሊያስጠርግ ሄደ፡፡ሰማዩን አየው፡፡ ከቤት ሲወጣ በደመና የተሸፈነ ነበር፡፡ አሁን
ግን ጥርት ብሏል፡፡ የሱ ስሜት ግን እንደሰማዩ አልጠራም፡፡ ፊቱ ጨፍግጓል፡፡ ጫማውን አስጠርጐ ወደ መሥሪያ ቤቱ ግቢ ሲዘልቅ......
“እንደምን አደርክ ሻምበል መልዕክት አለህ” አዳሪው ፖሊስ ከኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ፖስታ አቀበለው፡፡
ሻምበል ፖስታውን ተቀብሎ ተመለከተው፡፡ የላኪው ሥም
የለበትም፡፡
የአደራ ደብዳቤነቱን እንጂ ከማን እንደተላከ አይገልጽም፡፡
“ማን ነው የሰጠህ?” ሲል ፖሊሱን ጠየቀው፡፡ ስሟን እንዳልነገረችው ገለፀለት፡፡ በቀጥታ ወደ ቢሮው ሄደ፡፡
የቢሮውን መስኮት ከፈተው፡፡ ንፁህ አየር ገባ፡፡ ከዚያም
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ።
ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች። ናፍቆቷን ሙሉውን ሌሊት አቅፋት በመተኛት ተወጣች፡፡
አሁን ሁሉንም ጣጣዋን ጨርሳለች፡፡ ዕቅዷን ልትፈጽም ሰዓቱ እየደረሰ ነው፡፡ በሌሊት ተነስታ ልብሷን ለባብሳ ጨረሰችና፣ ከፔርሙስ ትንሽ አጥሚት ቀድታ ካጠጣቻት በኋላ፤ “ወደ ቤት ልሂድ እማ!” ብላ ለመሄደ ተነሳች፡፡
ደግማ፤ ደጋግማ፤ ጉንጮቿን አገላብጣ ሳመቻትና፤ ወጣች፡፡ስትወጣ መንፈሷ ሁሉ ጠንካራ ነበር፡፡ ፍርሀት ጓዙን ጠቅልሎ ነው የሄደው፡፡ ቤት ደርሳ ያንን ትናንትና በፍቅር ስታሽሞነሙነው የዋለችውን የአባቷን ቅርስ ሸፋፍና፤ በቦርሳዋ ይዛ፤ ወደ መርካቶ ገሰገሰች፡፡
እዚያ እፍልሚያው ቦታ ስትደርስ ከታክሲ ወረደችና ራቅ ብላ ዓይኖቿን በሱቁ ላይ ተክላ ትጠባበቅ ጀመር፡፡
ልቧ ድው! ድው፤ ይላል፡፡ እልህና ሲቃ ይተናነቋታል፡፡ እንዷ ደቂቃ አቤት ርዝመቷ! አውሬው ወጥመዱ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ በንቃት መጠባበቋን ቀጠለች፡፡
አንዳንድ ሱቆች መከፈት ጀምረዋል፡፡ እምብዛም ሰው አይታይም፡፡ መርካቶ ትንሽ ሞቅ ሲል እንደዚያ እንደማይተራመስ ሁሉ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያስገርም ነው፡፡
ነጠላዋን ተሸፋፍና፣ መንገደኛ መስላ፧ አንድ ጥግ ላይ ተቀመጠችና፤ ግዳይዋን መጠባበቁን ተያያዘችው፡፡ በእርግጥም ስለቸኮለች ነው መሰል በጣም ቀድማ ነበር የመጣችው፡፡
ገንዘብ በገፍ እየገባለት የመጣው ጎረምሳ በንግዱ ላይ ትኩረቱን እየጣለ ሄዶ ነበር፡፡ አበራን ወደዚያ ካባረረ በኋላ ትርፉን ለግሉ ማግበስበስ ጀምሯል።
ገንዘብ ሲቀምሱት ይጣፍጣል፡፡ በላይ በላዩ ያስመኛል። እህል ሲጠግቡት ያስገሳል፡፡ሲበዛም ያስጠላል፡፡ ገንዘብ የሚጠግብ ሆድ ግን የለም፡፡ ግሳትም የለው፡፡ በላይ በላዩ ጨምሩልኝ፣ ጨምሩልኝ፣ የሚያሰኝ፣ እየበሉት የሚርብ ነገር ቢኖር ገንዘብ ነው፡፡
እንደሻው የራሱ የሆነውን፤ እንደፈለገው የሚያዝበትን ገንዘብ ሲያገኝ፤ እንደጠላት ገንዘብ ማውደም ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ ሱቁን በማደራጀት ሀብታም መሆን ስለፈለገ፣ ቆጣቢና ትጉህ ሠራተኛ ሆኗል።
ዛሬ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ገበያ ሊሻማ መጣና የሱቁን በር ከፈተ፡፡ ሙሉ ጂንስ ለብሷል፡፡ ከላይ ጥቁር ክብ ባርኔጣ አድርጓል፡፡
አንገቱ ላይ አጠር ያለች ወፍራም ሻርፕ ጠምጥሞ ነበር፡፡
የሱቁን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ መዝለቁን ስታይ ትህትና ተዘጋጀች፡፡ እሷም ጂንስ ሱሪ ነው የለበሰችው፡፡
ቀስ ብላ ቀኝ እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰደደችና፣ ማጥበቂያውን አላላች፡፡ ሽጉጡ ላግዳጁ ዝግጁ ሆነ፡፡ አሁንም ቀስ ብላ ጨበጠቸው፡፡ እጇ የተንቀጠቀጠ መሰላት፡፡
“አይዞሽ ትህትና ጠንከር በይ” አለች ለራሷ፡፡ “የመጨረሻው ሰዓት የድል ሰዓት ደርሷል፡፡ የመጨረሻውን የድል ሰዓት ባትወጪው አበቃልሽ!” አለችና ራሷን አደፋፈረች፡፡
ይህ የመጨረሻው መክሸፍ የሌለበት እርምጃ ነው፡፡ በእውነትም ጠንከር አለች፡፡ ልቧ በትክክል መምታት ጀመረ፡፡ ሰውነቷ መራራ ደም ሲረጭ ተሰማት፡፡ የቀድሞ ባህሪዋ ከውስጧ ጥርግርግ ብሎ ወጣና፤ አዲስ የቆራጥነት፣ የደፋርነትና፤ የጭካኔ ባህሪይ ተላበሰች፡፡
“አምላኬ በደሌን አንተ ይቅር በለኝ፡፡ ነፍሴን ተቀበላት!” አለችና የሽጉጡን ምላጭ እንደያዘች እየተንደረደረች ወደ ሱቁ ሩጫዋን ቀጠለች፡፡
ሱቁ በር ላይ ስትደርስ እንደሻው በሚያየው ነገር ተደናግጦ፣ ዐይኖቹ ተበልጥጠው፣ አፉ ተከፍቶ እንደቀረ ትንፋሽ ከማውጣቱ በፊት
ሽጉጡን ላጥ አድርጋ አወጣችው፡፡
ንግግር የለ፣ ግርግር የለ፣ ፋታ ሳትሰጠው በቀጥታ እርምጃውን ወሰደች፡፡
ዷ! ዷ! ዷ! ዷ! አምስት የቆጠረች መሰላት፡፡ አራንቱን ጥይቶች ካንጣጣችበት በኋላ፣ ተንገዳግዶ መውደቁን ስታረጋግጥ፧ ሽጉጡን
ወደራሷ አዙራ አፍዋ ውስጥ አስገባቸው፡፡
ሰው መሯሯጥ ጀመረ፡፡ ለሚተራመሰው ሰው ቦታ ሳትሰጥ፤
እርምጃዋን በራሷ ላይ ወሰደች፡፡ ምላጩን ሳበቸው፡፡ ዷ! ዷ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ የተባዘተ ጥጥ በመሰለው ደመና ተዥጐርጉሯል።
ጨረሯን የፈነጠቀችው ፀሐይ ያንን የደመና ቁልል እየናደችው ስትመጣ፤
ሰዓሊው በሸራ ላይ በብሩሹ የፈነጠቀው ንድፍ እየመሰለ ሄደ፡፡ ከዚያም ሙሉ ለሙሉ ደመናው ተገፈፈና፤ ጥርት ያለ ሰማይ ታየ፡፡
የሰው ልጅ የውስጥ ስሜቱ ሲጐዳ፣ ሲከፋው፣ ሲጨንቀው፤ ልክ ሰማዩ በደመና እንደሚያኮርፈው ሁሉ፤ ይህንን መጥፎ የውስጥ ስሜቱን በጨፈገገ ገጽታው ይገልጸዋል፡፡ በሆነ ባልሆነው ሆደ ባሻነት ያጠቃዋል፡፡
እነሆ ልቡ ከአምስት ዓመታት በላይ ከፍቅር ተገልሎ የቆየው ሻምበል ብሩክ ትህትናን ካገኘበት እለት ጀምሮ መንፈሱ ታድሶ!
የወደፊት የትዳር ህይወቱን በቅርብ ርቀት አሻግሮ መመልከት ሲጀምር፤ በእንጭጩ ተቀጨ፡፡
ትህትና ፍቅሯን ብቻ ሳይሆን፤ ያንን ደስተኛነቱን ጭምር በልቡ ውስጥ ገድላበት ነው የሄደችው፡፡
ድምጿን ለመስማት ይፈልጋል፣ ወዲያውኑ ደግሞ ከነመፈጠሯ እንዲረሳት ይመኛል፡፡ ትናፍቀዋለች፤ የሠራችው በደል ፊቱ ላይ ድቅን
ይልበታል፡፡ በቅናት ይቃጠላል፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ ብሩኬ.... ብሩኬ....
ብሩኬ.... የሚለው ያ ለስላሳ ድምጿ፣ ያ ለስላሳ ሰውነቷ ያ ለስላሳ ባህሪዋ፤ ይታወሰዋል፡፡
በፊት የነበረችው ትህትና እንዴት የምትወደድ ልጅ ነበረች? ለምን ፈጣሪ አሳይቶ ነሳው? ምነው እሱ ለፍቅር አልታደለ? ሁል ጊዜ መጨነቅ?
“ምነው የዚያን ዕለት ባልተገናኘን ኖሮ” የሚል ሃሣብ መጣበት፡፡ ሆኖም በመገናኘታቸው አንድ መልካም ሥራ መስራቱ ያስደስተዋል፡፡
አጋር ያልነበራት እናቷን መርዳት መቻሉ እርካታን ይሰጠዋል።
ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም፡፡ እንዲሉ፣ እሷ ትበድለው እንጂ፤ እሱ ከበደል ይልቅ መልካም ሥራን የሠራ ተበዳይ መሆኑ ሲታወሰው፤ “ይሁን እስቲ ሁሉ ነገር ከፈጣሪ ይገኛል” ይልና
ይጽናናል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ የሰሞኑ ሁኔታው የተለየ ነበር፡፡ ናፍቆቷ ነፍሱን ሊያወጣው ደርሷል፡፡
በውስጡ ፍቅርና ጥላቻ ነግሰውበታል፡፡ እንዳይጠላት ይወዳታል፣ እንዳይወዳት ደግሞ የሠራችው ሥራ...እንዳንድ ጊዜ ያ አለቃቀሷ፤ እዚያ እላዩ ላይ ተጠምጥማ እየተንሰቀሰቀች የተናገረችው ንግግር፣ ትዝ ይለውና፤ “ምን ነበረበት ይቅር ብላት ኖሮ? ግብዝ ነኝ” በማለት እራሱን
ይኮንናል፡፡ ወዲያው ደግሞ የሻክረና ጥርጣሬ የገባው ልብ ተመልሶ ልብ
ላይሆን፡፡ የነቃ ብርሌ ተመልሶ ዕቃ ላይሆን፣ አጉል ሙጥኝ አለማለቱን
ይወደውና..
እንኳንም በጊዜ አቋረጥን” የሚል ስሜት ይሰማዋል፡፡በጠዋቱ መ/ቤቱ እንደደረሰ ወደ ቢሮ ከመግባቱ በፊት ጫማውን
ሊያስጠርግ ሄደ፡፡ሰማዩን አየው፡፡ ከቤት ሲወጣ በደመና የተሸፈነ ነበር፡፡ አሁን
ግን ጥርት ብሏል፡፡ የሱ ስሜት ግን እንደሰማዩ አልጠራም፡፡ ፊቱ ጨፍግጓል፡፡ ጫማውን አስጠርጐ ወደ መሥሪያ ቤቱ ግቢ ሲዘልቅ......
“እንደምን አደርክ ሻምበል መልዕክት አለህ” አዳሪው ፖሊስ ከኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ፖስታ አቀበለው፡፡
ሻምበል ፖስታውን ተቀብሎ ተመለከተው፡፡ የላኪው ሥም
የለበትም፡፡
የአደራ ደብዳቤነቱን እንጂ ከማን እንደተላከ አይገልጽም፡፡
“ማን ነው የሰጠህ?” ሲል ፖሊሱን ጠየቀው፡፡ ስሟን እንዳልነገረችው ገለፀለት፡፡ በቀጥታ ወደ ቢሮው ሄደ፡፡
የቢሮውን መስኮት ከፈተው፡፡ ንፁህ አየር ገባ፡፡ ከዚያም
👍1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....አፓርትመንቷ ጋ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ እጥፍ ብሎ ከአንድ ትንሽ ሻይ ቤት ገባና በሩ አጠገብ ካለ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሻይ አዘዘ፡፡ ጥንቃቄ ያስፈልጋል እርጋታ፡፡ ባሻገር የሚታየው የአፓርትመንቱ ቅጥር ግቢ አለቅጥ ጭር ብሏል፡፡ የወትሮው ግርግር ወጪና ገቢ አይታይም፡፡ ከአፓርትመንቱ ስር መኪናዎች በስርኣት ተደርድረው ቆመዋል፡፡ ለወትሮው ሲሯሯጠ የሚታዩ ሲጫወቱ የሚገኙ የአፓርትመንቱ ነዋሪዎች ልጆች በግቢው አይታዩም፡፡በር ላይ ብቻ እኛው የድሮው ሽማግሌ ዘበኛ አፈርማ ካፖርታቸውን ደርበው ከዘበኛዋ ቤት ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለው ያንጎላጃሉ፡፡
ይህ ነው ብሎ ምክንያት ሳይሰጠውም ፍርሃት ገባው፡፡ ፀጥታ ተራ ነገር አይደለም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሙሉ ፀጥታ አደጋ ከመድረሱ በፊት የሚያንዣብብ ማዘናጊያና አደጋው ከደረሰ በኋላ ድንጋጤን ደርቦ የሚንጠለጠል ግግርት ነው፡፡ ጥፍሩን መቆረጣጠም ጀመረ። ጭንቅላቱ ግራና ቀኝ ቆሞ ይሟገት ጀመር፡፡
ሰዓቱን ተመለከተ አሥራ ሁለት ከሃያ፡፡
ዝም ብዬ ነውኮ ይልቅ ብሎ ገብቼ እይቻት ብወጣ ይሻላል...ግን በአካባቢው የአውሬው አይን ቢኖርስ ስገባ ቢያየኝስ?ወዲያው ቢከቡኝስ ታዲያ እስከመቼ እዚህ ተቀምጨ እቆያለሁ?! ስልክ ደውዩ
ወንድሟን «ውጣ» ብለውስ ከአፓርትመንቱ እራቅ እንዲል ነግሬው
ባነጋግረውስ ምን ዋጋ አለው? ገብቼ ካላየኋትማ ለምንስ መጣሁ? ብገባ
ይሻላል... አዎ አይቻት ቶሉ እወጣለሁ… በአካባቢው ካሉ ግን ያለጥርጥር
እንደ ጅግራ ነው ክንፌን ብለው የሚጥሉኝ…ምን ዘዴ መፍጠር ይሻላል?
ጭንቅላቱን አፋጨው፡፡ አካባቢው እየጨለመ መጣ፡፡ የመንገድ
መብራቶች ቦግ ቦግ ቢሉም ደቂቃዎች በሄዱ ቁጥር ይበልጥ የሚደምቀውን
ጨለማ መታገል ማሸነፍ መግፈፍ እያቃታቸው መጠ፡፡ ናትናኤል ያለበትን
ክፍል ቃኘው፡፡ ትንሿ የሻይ ቤት ንጽህና የሌላት ናት፡፡ . በውስጧ የተሰበሰቡትም ሰዎች እሱው?እንዳጠለቀው በህይት የተጨማለቀ የጋራዥ ቱታ ቆሻሻ ልብስ የለበሱ ቀዝቅተኛ ኑሮ የሚገፉ፤ የሚጎትቱ እንደሆነ “ ያስታውቃሉ፡፡ ሰዓቱን ድጋሚ ተመለከተ፡፡ አስራ ሁለት ተኩል፡፡
በተቀመጠበት እንዳለ አሻግሮ የአፓርትመቱን መግቢያ በር ቃኘው፡፡ በሩቅ በድንግዝግዝ አንድ ሰው ይታየዋል፡፡ የበሩን አንድ ወገን መቃን ተደግፎ ቆሟል ሰውየወ:: ናትናኤል አትካር ተመለከተው፤ ካፖርት ለብሶ
አንገተዬውን ቀልብሶ የቆመውን ሰው ግን ሊለየው አልቻለም፡፡
'ብስራት ይሆን? መሆን አለበት። አሰበ፡፡
ተነስቶ ወደ አፓርትመንቱ መሄድ ግን ፈራ፡፡ ድጋሚ ዞር አለና እሱ ከተቀመጠበት ስፍራ ፈንጠር ብሎ ሁለት ክንዶቹን ጠረጴዛ ላይ ተክሎ
ጉንጭጮቹን በሁለት መዳፎቹ ደግፎ የተቀመጠ ጎረምሳ ላይ አተኮረ፡፡ አንድ
ዘዴ መጣለት:: ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ ወጣቱ ተጠጋ፡፡
“ሰላም...ልቀመጥ?” አለ ከወጣቱ ጠረጴዛ ዙሪያ ከተደረደሩት ሦስት
ወንበሮች አንዱን ያዝ ኣድርጎ፡፡
ወጣቱ ጉንጮቹን ዘሁለት መዳፎቹ ውስጥ ሳያወጣ አይኑን ብቻ
አቅንቶ ተመለከተው::
“ተቀመጥ:: አለ ወጣቱ ግድ እንደሌለው ለማሳየት ትከሻውን ከፍ ዝቅ አድርጎ፡፡
“እንድ የምትሰራልኝ ስራ ነበር፡፡ በቂ ገንዘብ እከፍልሃለሁ፡፡” አለ ናትናኤል ከኪሱ ቦርሳወን አውጥቶ ሁለት የአስር ብር ኖቶች እየመዘዘ፡፡
ከፊት ለፊቱ የተቀመጠው ወጣት ቀያዮቹን ኖቶች ሲመለከት ጉንጮቹን ለቀቅ አደረገና ቀና አለ፡፡ የደረበው ረጅም አሮጌ ኮት አንገትዬው ነትቧል፤ ከውስጥ ሸሚዞ በሽቅጧል፡፡
“ትስማማለህ?”
“ምንድነው የምሰራልህ? የሚደበደብ ሰው ከሆነ እርሳው፡፡” አለ ወጣቱ አገጩ ላይ ችፍርግ ብሎ የበቀለውን የቆሽሽ ጺም እያከከ፡፡
“አይደለም፡፡” አለ ናትናኤል ወደፊት ጠጋ ብሎ “እየው ያ ፎቅ ይታይሃል? በሩ ላይ የቆመው ሰውዬ ይታይሃል?”
ወጣቱ በ'አዎንታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡
“…ቀጥ ብለህ ወደ ሰውየው ትሄድና አጠገቡ ልትደርስ ጥቂት
እርምጃዎች ሲቀርህ ናትናኤል ይፈልግሃል። ተከተለኝ በለውና ድንገት
ፊትህን መልሰህ እየሮጥክ ከግቢው ወጥተህ ትመጣለህ፡፡”
“እናስ.. ከዛ በኋላስ?”
“በቃ::”
“እንዴት በቃ? እለ ወጣቱ ፊቱ ጥርጣሬ ለብሶ:: “እዛች ደርሼ ስለተመለስኩ ነው ይህን የምትሰጠኝ?” ወጣቱ፡፡ ዓይኖቹን በሁለቱ፡ የአስር ብር ኖቶች ላይ አነጣጠራቸው፡፡
“አዎ::"
“ምንም ሳልሰራ?”
“አዎ፡፡”
“አትቀልድ፡፡ ነገር አለው፡፡” አለ ጎረምሳው ወደ አንድ ወገን እየሳቀ፡፡
“ምንም ነገር የለውም፡፡”
ወጣቱ ኣይኖቸን አጥብቦ ናትናኤልን ሊያጠናው ሞከረ::
“ለምን እራስህ አትሄድም?"
“ትፈልጋለህ አትፈልግም?” አለ ናትናኤል ሁለቱን የአስር ብር ኖቶች ወደፊት እየገፋ::
ወጣቱ፡ ከራሱ ጋር ክርክር የገጠመ መሰለ፡፡ ናትናኤል ድንገት ትቶት ሲነሳ ፈጠን ብሎ አብሮት ተነሳ፡፡
“እሺ አምጣ፡፡ ፀጥ ብዬ ገብቼ ናትናኤል ያጠራሃል ብዬው ፀጥ ብዬ መወጣት ነው… እይደል?”
“እየሮጥክ ነው የምትወጣው፤ ፀጥ ብለህ አያደለም:: ልክ ከሰውየው እንደምትሸሽ ዓይነት እየሮጥክ፡፡” ናትናኤል ቆፍጠን አለ ሃያ ብር
የያዘውን ቀኝ እጁን ወደኋላ ሰብስቦ፡፡
“እሺ ኣምጣ…. እሮጣለሁ፡፡” አለ ወጣቱ እጁን ወደ ብሩ ዘርግቶ፡፡
“ደርስህ ስትመለስ…. መሮጥሀን ካየሁ በኋላ፡፡” ናትናኤል ፈርጠም አላ::
“እሺ ግማሹን ስጠኝ::”
“ደርሰህ ስትመለስ መሉው ያንተ ነው፡፡”
ወጣቱ ከሻይ ቤቷ ወጥቶ ወደ አፓርትመንቱ ሲያመራ ናትናኤል
ተከትሎት ወጣና የመኪና መንገዱን ተሻግሮ ከለላ ይዞ የሚሆነውን
ይከታተል ጀመር፡፡
የሚጠባበቁት ሰዎች ካሉ ወደ አፓርትመንቱ ሲገባ ሊይዘት ወጥመድ ያጠመዱ ካሉ። ወጥመዳቸው በወጣቱ ላይ እንደሚወነጨፍ እርግጠኛ ነበር፡፡
ወጣቱ የአፓርትመንቱን የአጥር ግቢ በር አልፎ ሲገባ ሽማግሌው ዘበኛ ከእንቅልፋቸው አልነቁም:: ወጣቱ እጆቹን የኮት ከሶቹ ውስጥ ከትቶ በእርጋታ አፓርትመንቱ በር ላይ ወደቆመው ሰው አመራ፡፡ ሰውዬውጋ ለመድረስ በግምት አአስር እርምጃዎች ሲቀሩት ድንገት ቆም አለና ናትናኤል እንዳዘዘው መልዕክቱን ተንፍሶ ፊቱን መልሶ ሮጥ ከማለቱ፡ ግራና ቀኝ ቆመው የነበሩ መኪናዎች በሮች እየተበረገዱ አራት ሰዎች ዱብ ዱብ አሉ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን አፍጥጦ ቀረ፡፡ በሁኔታው የተደናገጠው ወጣት
ለማምለጥ ቢሞክርም ከአጥር ግቢው በር ከመድረሱ በፊት ይዘው እፍስፍጥ
አድርገው ከአንደኛዋ መኪና ውስጥ ከተቱት፡፡
ለደቂቃዎች ናትናኤል ካለበት ሳይንቀሳቀስ ተጠባበቀ፡፡ ወዲያው
የመኪናዋ በር ተከፈተና በሁለት በኩል የወጣቱን ክንዶች የልጨመደዱ ሁለት
ሰዎችና ሌሎች ተጨጨማሪ ሶስት ሰዎች ወደ አፓርትመንቱ፡ ግቢ በር ያጣደፉ ጀመር፡፡ ከአፓርትመንቱ፡ ግቢ ሲወጡ ናትናኤል ወደ ኋላ አፈገፈገና ጥሩ ከለላ ይዞ በሩቁ በአይኑ ያስተውላቸው ጀመር::
አምስቱ ሰዎች ወጣቱን ከበው ወደ ሻይ ቤቷ ተጣደፉ፡፡ ከሻይ ቤቷ ደጃፍ፡ እንደደረሱ ሀለቱ ልጁን አስቀድመን ከተል ብለው ሲገቡ ሁለቱ፡፡ በሻይ ቤቷ ጓሮ ዞሩ፡፡ የተቀረው አምስተኛው እፊት ለፊት ጀርባውን ግድግዳው ላያ ለጥፎ ቀኝ እጁን ከኮቱ፡ ስር ብብቱ ስር ከቶ ቆመ::
ናትናኤል ሰውየው ከኮቱ ስር የጨበጠው ምን እንደሆነ ሲረዳ አብርሃም ታወሰው፡፡ ሻይ ቤቷ ውስጥ የቡት ሰዎች ከውስጥ ሲያጡት ወጥተው አካበቢውን ሊያስሱ እንደሚችሉ ሲረዳ ፈጠን ብሎ ከተደበቀበት ወጣና ሽቅብ በሩጫ ተፈተለኩ ታክሲ ተራ ደርሶ ለገሃር ብሎ ታክሲው ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ሁሉ ሁለት ሦስቴ እየተገላመጠ ተመለከተ፡፡ ከጀርባው የተከተለው ሰው ግን አልነበረም፡፡ ወደኋላ መመለስ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....አፓርትመንቷ ጋ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ እጥፍ ብሎ ከአንድ ትንሽ ሻይ ቤት ገባና በሩ አጠገብ ካለ ወንበር ላይ ተቀምጦ ሻይ አዘዘ፡፡ ጥንቃቄ ያስፈልጋል እርጋታ፡፡ ባሻገር የሚታየው የአፓርትመንቱ ቅጥር ግቢ አለቅጥ ጭር ብሏል፡፡ የወትሮው ግርግር ወጪና ገቢ አይታይም፡፡ ከአፓርትመንቱ ስር መኪናዎች በስርኣት ተደርድረው ቆመዋል፡፡ ለወትሮው ሲሯሯጠ የሚታዩ ሲጫወቱ የሚገኙ የአፓርትመንቱ ነዋሪዎች ልጆች በግቢው አይታዩም፡፡በር ላይ ብቻ እኛው የድሮው ሽማግሌ ዘበኛ አፈርማ ካፖርታቸውን ደርበው ከዘበኛዋ ቤት ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለው ያንጎላጃሉ፡፡
ይህ ነው ብሎ ምክንያት ሳይሰጠውም ፍርሃት ገባው፡፡ ፀጥታ ተራ ነገር አይደለም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሙሉ ፀጥታ አደጋ ከመድረሱ በፊት የሚያንዣብብ ማዘናጊያና አደጋው ከደረሰ በኋላ ድንጋጤን ደርቦ የሚንጠለጠል ግግርት ነው፡፡ ጥፍሩን መቆረጣጠም ጀመረ። ጭንቅላቱ ግራና ቀኝ ቆሞ ይሟገት ጀመር፡፡
ሰዓቱን ተመለከተ አሥራ ሁለት ከሃያ፡፡
ዝም ብዬ ነውኮ ይልቅ ብሎ ገብቼ እይቻት ብወጣ ይሻላል...ግን በአካባቢው የአውሬው አይን ቢኖርስ ስገባ ቢያየኝስ?ወዲያው ቢከቡኝስ ታዲያ እስከመቼ እዚህ ተቀምጨ እቆያለሁ?! ስልክ ደውዩ
ወንድሟን «ውጣ» ብለውስ ከአፓርትመንቱ እራቅ እንዲል ነግሬው
ባነጋግረውስ ምን ዋጋ አለው? ገብቼ ካላየኋትማ ለምንስ መጣሁ? ብገባ
ይሻላል... አዎ አይቻት ቶሉ እወጣለሁ… በአካባቢው ካሉ ግን ያለጥርጥር
እንደ ጅግራ ነው ክንፌን ብለው የሚጥሉኝ…ምን ዘዴ መፍጠር ይሻላል?
ጭንቅላቱን አፋጨው፡፡ አካባቢው እየጨለመ መጣ፡፡ የመንገድ
መብራቶች ቦግ ቦግ ቢሉም ደቂቃዎች በሄዱ ቁጥር ይበልጥ የሚደምቀውን
ጨለማ መታገል ማሸነፍ መግፈፍ እያቃታቸው መጠ፡፡ ናትናኤል ያለበትን
ክፍል ቃኘው፡፡ ትንሿ የሻይ ቤት ንጽህና የሌላት ናት፡፡ . በውስጧ የተሰበሰቡትም ሰዎች እሱው?እንዳጠለቀው በህይት የተጨማለቀ የጋራዥ ቱታ ቆሻሻ ልብስ የለበሱ ቀዝቅተኛ ኑሮ የሚገፉ፤ የሚጎትቱ እንደሆነ “ ያስታውቃሉ፡፡ ሰዓቱን ድጋሚ ተመለከተ፡፡ አስራ ሁለት ተኩል፡፡
በተቀመጠበት እንዳለ አሻግሮ የአፓርትመቱን መግቢያ በር ቃኘው፡፡ በሩቅ በድንግዝግዝ አንድ ሰው ይታየዋል፡፡ የበሩን አንድ ወገን መቃን ተደግፎ ቆሟል ሰውየወ:: ናትናኤል አትካር ተመለከተው፤ ካፖርት ለብሶ
አንገተዬውን ቀልብሶ የቆመውን ሰው ግን ሊለየው አልቻለም፡፡
'ብስራት ይሆን? መሆን አለበት። አሰበ፡፡
ተነስቶ ወደ አፓርትመንቱ መሄድ ግን ፈራ፡፡ ድጋሚ ዞር አለና እሱ ከተቀመጠበት ስፍራ ፈንጠር ብሎ ሁለት ክንዶቹን ጠረጴዛ ላይ ተክሎ
ጉንጭጮቹን በሁለት መዳፎቹ ደግፎ የተቀመጠ ጎረምሳ ላይ አተኮረ፡፡ አንድ
ዘዴ መጣለት:: ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ ወጣቱ ተጠጋ፡፡
“ሰላም...ልቀመጥ?” አለ ከወጣቱ ጠረጴዛ ዙሪያ ከተደረደሩት ሦስት
ወንበሮች አንዱን ያዝ ኣድርጎ፡፡
ወጣቱ ጉንጮቹን ዘሁለት መዳፎቹ ውስጥ ሳያወጣ አይኑን ብቻ
አቅንቶ ተመለከተው::
“ተቀመጥ:: አለ ወጣቱ ግድ እንደሌለው ለማሳየት ትከሻውን ከፍ ዝቅ አድርጎ፡፡
“እንድ የምትሰራልኝ ስራ ነበር፡፡ በቂ ገንዘብ እከፍልሃለሁ፡፡” አለ ናትናኤል ከኪሱ ቦርሳወን አውጥቶ ሁለት የአስር ብር ኖቶች እየመዘዘ፡፡
ከፊት ለፊቱ የተቀመጠው ወጣት ቀያዮቹን ኖቶች ሲመለከት ጉንጮቹን ለቀቅ አደረገና ቀና አለ፡፡ የደረበው ረጅም አሮጌ ኮት አንገትዬው ነትቧል፤ ከውስጥ ሸሚዞ በሽቅጧል፡፡
“ትስማማለህ?”
“ምንድነው የምሰራልህ? የሚደበደብ ሰው ከሆነ እርሳው፡፡” አለ ወጣቱ አገጩ ላይ ችፍርግ ብሎ የበቀለውን የቆሽሽ ጺም እያከከ፡፡
“አይደለም፡፡” አለ ናትናኤል ወደፊት ጠጋ ብሎ “እየው ያ ፎቅ ይታይሃል? በሩ ላይ የቆመው ሰውዬ ይታይሃል?”
ወጣቱ በ'አዎንታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ፡፡
“…ቀጥ ብለህ ወደ ሰውየው ትሄድና አጠገቡ ልትደርስ ጥቂት
እርምጃዎች ሲቀርህ ናትናኤል ይፈልግሃል። ተከተለኝ በለውና ድንገት
ፊትህን መልሰህ እየሮጥክ ከግቢው ወጥተህ ትመጣለህ፡፡”
“እናስ.. ከዛ በኋላስ?”
“በቃ::”
“እንዴት በቃ? እለ ወጣቱ ፊቱ ጥርጣሬ ለብሶ:: “እዛች ደርሼ ስለተመለስኩ ነው ይህን የምትሰጠኝ?” ወጣቱ፡፡ ዓይኖቹን በሁለቱ፡ የአስር ብር ኖቶች ላይ አነጣጠራቸው፡፡
“አዎ::"
“ምንም ሳልሰራ?”
“አዎ፡፡”
“አትቀልድ፡፡ ነገር አለው፡፡” አለ ጎረምሳው ወደ አንድ ወገን እየሳቀ፡፡
“ምንም ነገር የለውም፡፡”
ወጣቱ ኣይኖቸን አጥብቦ ናትናኤልን ሊያጠናው ሞከረ::
“ለምን እራስህ አትሄድም?"
“ትፈልጋለህ አትፈልግም?” አለ ናትናኤል ሁለቱን የአስር ብር ኖቶች ወደፊት እየገፋ::
ወጣቱ፡ ከራሱ ጋር ክርክር የገጠመ መሰለ፡፡ ናትናኤል ድንገት ትቶት ሲነሳ ፈጠን ብሎ አብሮት ተነሳ፡፡
“እሺ አምጣ፡፡ ፀጥ ብዬ ገብቼ ናትናኤል ያጠራሃል ብዬው ፀጥ ብዬ መወጣት ነው… እይደል?”
“እየሮጥክ ነው የምትወጣው፤ ፀጥ ብለህ አያደለም:: ልክ ከሰውየው እንደምትሸሽ ዓይነት እየሮጥክ፡፡” ናትናኤል ቆፍጠን አለ ሃያ ብር
የያዘውን ቀኝ እጁን ወደኋላ ሰብስቦ፡፡
“እሺ ኣምጣ…. እሮጣለሁ፡፡” አለ ወጣቱ እጁን ወደ ብሩ ዘርግቶ፡፡
“ደርስህ ስትመለስ…. መሮጥሀን ካየሁ በኋላ፡፡” ናትናኤል ፈርጠም አላ::
“እሺ ግማሹን ስጠኝ::”
“ደርሰህ ስትመለስ መሉው ያንተ ነው፡፡”
ወጣቱ ከሻይ ቤቷ ወጥቶ ወደ አፓርትመንቱ ሲያመራ ናትናኤል
ተከትሎት ወጣና የመኪና መንገዱን ተሻግሮ ከለላ ይዞ የሚሆነውን
ይከታተል ጀመር፡፡
የሚጠባበቁት ሰዎች ካሉ ወደ አፓርትመንቱ ሲገባ ሊይዘት ወጥመድ ያጠመዱ ካሉ። ወጥመዳቸው በወጣቱ ላይ እንደሚወነጨፍ እርግጠኛ ነበር፡፡
ወጣቱ የአፓርትመንቱን የአጥር ግቢ በር አልፎ ሲገባ ሽማግሌው ዘበኛ ከእንቅልፋቸው አልነቁም:: ወጣቱ እጆቹን የኮት ከሶቹ ውስጥ ከትቶ በእርጋታ አፓርትመንቱ በር ላይ ወደቆመው ሰው አመራ፡፡ ሰውዬውጋ ለመድረስ በግምት አአስር እርምጃዎች ሲቀሩት ድንገት ቆም አለና ናትናኤል እንዳዘዘው መልዕክቱን ተንፍሶ ፊቱን መልሶ ሮጥ ከማለቱ፡ ግራና ቀኝ ቆመው የነበሩ መኪናዎች በሮች እየተበረገዱ አራት ሰዎች ዱብ ዱብ አሉ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን አፍጥጦ ቀረ፡፡ በሁኔታው የተደናገጠው ወጣት
ለማምለጥ ቢሞክርም ከአጥር ግቢው በር ከመድረሱ በፊት ይዘው እፍስፍጥ
አድርገው ከአንደኛዋ መኪና ውስጥ ከተቱት፡፡
ለደቂቃዎች ናትናኤል ካለበት ሳይንቀሳቀስ ተጠባበቀ፡፡ ወዲያው
የመኪናዋ በር ተከፈተና በሁለት በኩል የወጣቱን ክንዶች የልጨመደዱ ሁለት
ሰዎችና ሌሎች ተጨጨማሪ ሶስት ሰዎች ወደ አፓርትመንቱ፡ ግቢ በር ያጣደፉ ጀመር፡፡ ከአፓርትመንቱ፡ ግቢ ሲወጡ ናትናኤል ወደ ኋላ አፈገፈገና ጥሩ ከለላ ይዞ በሩቁ በአይኑ ያስተውላቸው ጀመር::
አምስቱ ሰዎች ወጣቱን ከበው ወደ ሻይ ቤቷ ተጣደፉ፡፡ ከሻይ ቤቷ ደጃፍ፡ እንደደረሱ ሀለቱ ልጁን አስቀድመን ከተል ብለው ሲገቡ ሁለቱ፡፡ በሻይ ቤቷ ጓሮ ዞሩ፡፡ የተቀረው አምስተኛው እፊት ለፊት ጀርባውን ግድግዳው ላያ ለጥፎ ቀኝ እጁን ከኮቱ፡ ስር ብብቱ ስር ከቶ ቆመ::
ናትናኤል ሰውየው ከኮቱ ስር የጨበጠው ምን እንደሆነ ሲረዳ አብርሃም ታወሰው፡፡ ሻይ ቤቷ ውስጥ የቡት ሰዎች ከውስጥ ሲያጡት ወጥተው አካበቢውን ሊያስሱ እንደሚችሉ ሲረዳ ፈጠን ብሎ ከተደበቀበት ወጣና ሽቅብ በሩጫ ተፈተለኩ ታክሲ ተራ ደርሶ ለገሃር ብሎ ታክሲው ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ሁሉ ሁለት ሦስቴ እየተገላመጠ ተመለከተ፡፡ ከጀርባው የተከተለው ሰው ግን አልነበረም፡፡ ወደኋላ መመለስ
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
...ኪም ቾይ ላና ግሬይ ከዶክተር ሮበርትስ ቢሮ ስትወጣ እንዳየቻት ኮምፒውተሯ ላይ እየተየበች እንደሆነ ማስመሰል ጀመረች።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ በኒሮ ሳይንስ ዲግሪዋን የያዘችው ኪም ቾይ የኒኪ ረዳት ሆና የትሬይን ቦታ ተክታ በመሥራት ላይ ትገኛለች፡፡ ኪም በጣም ጎበዝ እና ቆንጆ ናት፡፡ ለስላሳ የእስያ ቆዳ፣ ጎላ ጎላ ያሉ ዓይኖች እና ጥቁር ሀር የመሰለ ፀጉር አላት፡፡
ወግ አጥባቂ በሆነ የቻይና ቤተሰብ ውስጥ ስላደገችም የቀድሞ ታዋቂ
የቴሌቪዥን ተዋናይዋን ስታያት በጣም ነው የደነገጠችው።
“ሚሲስ ግሬይ ሌላ የቀጠሮ ጊዜ ልያዝልሽ?” ብላም ኪም ልቧ በጣም
እየመታባት ጠየቀቻት፡፡ ከዚህ በፊት ከታዋቂ ሰው ጋር በአካል ተገናኝታ
ስለማታውቅ ነበር ልቧ መምታቱ። ይኼ የትርፍ ጊዜ ስራዋ ብዙ ታዋቂ
ሰዎችን በአካል እንድታይ አድርጓታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ላይብረሪ ውስጥ
ከመንቀዋለል እዚህ መዋሏ በጣም ደስ የሚል ነገር ነው የሚፈጥርላት።
ላና ዞር ብላ ከዴስኩ ጀርባ የምትገኘውን ቀጭን ቆንጆ የእስያ ደም ያላትን ልጅም ስትመለከት ኃይለኛ ቅናት ጉሮሮዋን አነቃት፡፡ የራሷ የዶክተሯ አልበቃ ብሏት በየሳምንቱ ዶክተሯን ስታገኛት በእሷ ሕይወት እና ቁንጅና ማስቀናቷ አልበቃ አላት እና አሁን ደግሞ በጣም ቆንጆ ወጣትን ለቢሮዋ ቀጠረች።
'ይህን ነገር አውቃ ነው የምታደርገው?' ብላ ላና እያሰበች 'ለራሴ ያለኝን
ግምት ልታንኮታኩተው ትፈልጋለች ፤ ስለዚህም ይህንን የወደቀውን ለራሴ
ያለኝን ግምት ለማስተካከል ብዬ ወደ እሷ ስመላለስ እንግዲህ እሷ 300
ዶላሯን ላጥ ታደርጋለች ማለት ነው፡፡ ማን ይታመናል በዚህ ጊዜ ዶክተሯ ይህን አታደርግም አይባልም፡፡
ላናም ወደ ኪም ዴስክ ቀረበች እና ጎንበስ ብላ በተቆጣ ድምፅ “እኔ ሌላ ቀጠሮ መያዝ ብፈልግ እነግርሽ አልነበር እንዴ?” ብላ ጠየቀቻት፡፡
ኪምም በላና ምላሽ በጣም ደንግጣ ግራ ተጋባች፡፡ “ምናልባት የሐኪሟ ደምበኞች ሳይናገሩኝ ማናገር አይጠበቅብኝ ይሆን? ብላም አሰበች እኛ
“ይቅርታ ሚስስ ግሬይ እኔ ያሰብኩት...” አለቻት፡፡
ላናም በጣም ተናድዳ ወደ ዴስኩ ሄደችና ኪም ላይ አይኗን አጉረጥርጣ
“እኔ ቀጠሮ ስፈልግ እጠይቅሻለሁ። እንዲያውም ከዚህ በኋላ እዚህ አልመጣም” ብላት እየተቆናጠረች በሩን በሀይል ዘግታ ከእንግዳ መቀበያው
ክፍል ወጣች፡፡
የበሩን በሀይል መዘጋትን የሰማችው ኒኪም ከቢሮዋ ወጥታ የእንግዳ
መቀበያ ክፍሉ ውስጥ ስትገባ ረዳቷ ኪም ቾይን አይኗ እምባ አቅርሮ ተመለከተቻት፡፡
“ይቅርታ ዶክተር እኔ ላናን ሳላበሳጫት አልቀርም። ግን እኮ ቀጠሮ ልያዝልሽ ነው እንጂ ሌላ ምንም ነገር አላልኳትም፡፡”
“አይዞሽ እሷ ሁሌም እንደዚህ ናት” ብላ ኒኪ አፅናናቻት።
“ግን እኮ ሁለተኛ እዚህ አልመጣም ብላለች። ይቅርታ ሥራሽን አበላሽሁብሽ መሰለኝ” ብላ ኪም ቾይ ማልቀስ ጀመረች፡፡
“ኧረ አታልቅሺ፡፡ ታያለሽ በሚቀጥለው ሳምንት እራሷ ትመጣለች። አሁን ተረጋጊ፡ ሌላው ደግሞ ካርተር በርክሌይ እንደመጣ አስገቢው” አለቻት፡፡
ኒኪ ወደ ቢሮዋ ተመልሳ ወንበር ላይ ቁጭ ካለች በኋላ ባሏ በሕይወት
እያለ ያለማመዳትን የትንፋሽ ልምምድ ማድረግ ጀመረች።
አየር በኃይል ወደ ውስጥ ሳቢ የሚለው የባሏ ድምፅ በውስጧ ይሰማታል፡፡ ከዚያም ወረቀቶችሽን እየነጠልሽ እንደምታስቀምጪ ሁሉ
ሃሳቦችሽንም አንድ በአንድ በየተራ እየነጠልሽ አስቀምጪያቸው።
አየር በኃይል ወደ ውስጥ ሳበች እና የመጀመሪያውን ሃሳቧን ማሰብ ጀመረች ላናን ላግዛት አልቻልኩም፡፡ እሷ ሁሌም ወጣት ሴቶችን ባየች ቁጥር ንዴቷ እየጨመረ ነው የሚመጣው፡፡ ምናልባት ወደ ሌላ ቴራፒስት ልልካት ይገባል፡፡ ቴራፒስት ብቻ ሳይሆን ሳይካትሪስትም ሳያስፈልጋት አይቀርም፡፡ ግን እንዴት ልልካት እችላለሁ?'
ለሁለተኛ ጊዜ አየር በጣም ወደ ውስጥ ሳበች እና ስለእሷ ማሰብ ጀመረች፡፡ እኔ ጥሩ ቴራፒስትም ጥሩ ሚስትም አይደለሁም፡፡ ምክንያቱም ጥሩ ሚስት ብሆን ኖሮ ለባሌ አርግዤለት ልጅ እወልድለት ነበር፡፡ እሱም ሌላ ሰው ጋር ባልሄደ ነበር፡፡' ብላ አሰበች፡፡ በመቀጠልም “አሁን ስለራሴ
ሳይሆን ስለታካሚዎቼ ነው ማሰብ የሚገባኝ እያለች ሃሳቧን ልትጀምር
ስትል ቢሮዋ ግርግዳ ላይ ያለው የተረኛ ታካሚውን መምጣት የሚገልጸው
መብራት ብልጭ ድርግም ሲል ካርተር እንደመጣ አወቀች፡፡ ከወንበሯ
ተነስታም የቢሮዋን በር ከፈተች::
ኮሪደሩ ላይ ካርተር አንድ እግሩ በጀሶ ታስሮ እና በአንደኛው ወንበር መደገፊያም ላይም ሁለት ክራንቾቹን አስቀምጧል፡፡ የቢሮውን መከፈት እንዳየም በፍጥነት ሁለቱን ክራንቾቹን በግራና በቀኝ በኩል እየተደገፈ ወደ ቢሮው ውስጥ ገባ፡፡ ኒኪ በሩን ዘግታ ካርተር ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ምን ሆነህ ነው?” ብላ አስባለት ጠየቀችው፡፡
ፊቱ ላይ ላቡ ችፍ ብሎ ጠብታዎች ግንባሩ ላይ ሠርቷል፡፡ ጥርሱም
እየተንቀጫቀጨ ነው።
“በጥይት መተውኝ ነው!” አላት እና በፍርሃት ዓይን ያያት ጀመር፡፡
“በእግዚአብሔር ስም ማን ነው የመታህ? መቼ ነው ይኼ ነገር የተከሰተው?”
“ምናልባት አላማርኳቸው ይሆናል፡፡ ግን እነዚያ ሁሌም ስነግርሽ የነበሩት የሜክሲኮ ወሮበሎች ናቸው፡፡ ከዚህ ቀደም ቤቴ ገብተው የማስፈራሪያ ነገር መኝታ ቤቴ ውስጥ አስቀምጠው ነበር፡፡”
“ይህንን ደግሞ ፖሊሶች ጋር አመልክቼ ነበር፡፡ እነርሱ ግን እኔ ፈጥሬ የተናገርኩት ይመስል አላመኑኝም” አላት፡፡
ኒኪ ይህንን ስትሰማ ደነገጠች፡፡ ምክንያቱም እሷ ቤትም የሆነ ሰው
ከመኝታ ቤቷ ውስጥ የሚገኘውን የእሷና የባሏን የሠርግ ፎቶ እንደተወሰደባት ለፖሊሶች ብትነግርም እነርሱ ግን ችላ ያሉትን ነገር አስታወሰች፡፡
“እነርሱ እንደዚህ ቢያስቡም አያገባኝም፡፡ እናታቸውን... እኔ እውነታውን በደንብ ነው የማውቀው፡፡ በጥይት የተመታሁት ባለፈው ቅዳሜ ከክለብ ስወጣ ሌሊት ላይ ነው፡፡ በግምት ከሌሊቱ 7፡30 ላይ፡፡ ምናልባትም ይከታተሉን ስለነበር ያለሁበትን ቦታ አውቀውታል፡፡ እኔ ከክለቡ ወጥቼ መኪናዬን ፓርክ ያደረገው ሰው መኪናዬን እስኪያመጣልኝ ድረስ
እየጠበቅሁት ነበር፡፡ ይኼኔም አንድ መኪና ከአጠገቤ ቆመ እና ሁለት ሰዎች
ወጡ፡፡ አንደኛው ቅልጥሜ ላይ በጥይት ከመታኝ በኋላ መኪና ውስጥ
ገብተው መሬት ላይ ጥለውኝ ሄዱ፡፡”
ካርተር የደረሰበትን ነገር በፍጥነት ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ አሁንም
የደረሰበትን ነገር እያስታወሰ ጥርሱን ሲያንቀጫቅጭ ኒኪ ተመለከተችው፡፡
“በጥይት ሲመቱህ በአካባቢው ላይ ማንም አልነበረም?” ብላ ጠየቀችው፡፡
ካርተርም ጭንቅላቱን በአሉታ ወዝውዞ “ማንም አልነበረም ብቻዬን ነበርኩኝ፡ መኪናዬን ያቆመው ልጅም መኪናዬን ካቆመበት ቦታ ሊያመጣ ሄዶ ነበር፡፡ እሱ መኪናዬን ይዞ በመጣ ጊዜ እኔ መሬት ላይ ወድቄ ደሜን እያዘራሁ ከመሆኔም በላይ ራሴንም በመሳት ላይ ነበርኩኝ”
“መልካም” አለች ኒኪ፡፡ እንደሰው የነገራትን ነገር ማመን ይኖርባታል።
ምክንያቱም እሷን ለማሳመን ብሎ እግሩን በጀሶ እንደማያጅል ይገባታል፡፡
ምናልባት እንኳን የነገራት ነገር ውሽት ቢሆን እንኳን የራሱን ቅልጥም
በሽጉጥ መትቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ይህንን ለምን ያደርጋል? አትኩሮት
ፍለጋ ነው? ካርተር ደግሞ በዚህ መልኩ በሽታው ብሶበታል ብላ ኒኪ አታምንም፡፡ ምክንያቱም የባንክ ሥራውን በአግባቡ እየሰራ መሆኑን ታውቃለች
ስለሜክሲካኖቹ የወሮበሎች ቡድን በየጊዜው የሚያወራትን ነገር
ተጨባጭነት ባለው ምክንያት ሳያረጋግጥላት በጥይት ቅልጥሙን መቱት የሚለውን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
...ኪም ቾይ ላና ግሬይ ከዶክተር ሮበርትስ ቢሮ ስትወጣ እንዳየቻት ኮምፒውተሯ ላይ እየተየበች እንደሆነ ማስመሰል ጀመረች።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ በኒሮ ሳይንስ ዲግሪዋን የያዘችው ኪም ቾይ የኒኪ ረዳት ሆና የትሬይን ቦታ ተክታ በመሥራት ላይ ትገኛለች፡፡ ኪም በጣም ጎበዝ እና ቆንጆ ናት፡፡ ለስላሳ የእስያ ቆዳ፣ ጎላ ጎላ ያሉ ዓይኖች እና ጥቁር ሀር የመሰለ ፀጉር አላት፡፡
ወግ አጥባቂ በሆነ የቻይና ቤተሰብ ውስጥ ስላደገችም የቀድሞ ታዋቂ
የቴሌቪዥን ተዋናይዋን ስታያት በጣም ነው የደነገጠችው።
“ሚሲስ ግሬይ ሌላ የቀጠሮ ጊዜ ልያዝልሽ?” ብላም ኪም ልቧ በጣም
እየመታባት ጠየቀቻት፡፡ ከዚህ በፊት ከታዋቂ ሰው ጋር በአካል ተገናኝታ
ስለማታውቅ ነበር ልቧ መምታቱ። ይኼ የትርፍ ጊዜ ስራዋ ብዙ ታዋቂ
ሰዎችን በአካል እንድታይ አድርጓታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ላይብረሪ ውስጥ
ከመንቀዋለል እዚህ መዋሏ በጣም ደስ የሚል ነገር ነው የሚፈጥርላት።
ላና ዞር ብላ ከዴስኩ ጀርባ የምትገኘውን ቀጭን ቆንጆ የእስያ ደም ያላትን ልጅም ስትመለከት ኃይለኛ ቅናት ጉሮሮዋን አነቃት፡፡ የራሷ የዶክተሯ አልበቃ ብሏት በየሳምንቱ ዶክተሯን ስታገኛት በእሷ ሕይወት እና ቁንጅና ማስቀናቷ አልበቃ አላት እና አሁን ደግሞ በጣም ቆንጆ ወጣትን ለቢሮዋ ቀጠረች።
'ይህን ነገር አውቃ ነው የምታደርገው?' ብላ ላና እያሰበች 'ለራሴ ያለኝን
ግምት ልታንኮታኩተው ትፈልጋለች ፤ ስለዚህም ይህንን የወደቀውን ለራሴ
ያለኝን ግምት ለማስተካከል ብዬ ወደ እሷ ስመላለስ እንግዲህ እሷ 300
ዶላሯን ላጥ ታደርጋለች ማለት ነው፡፡ ማን ይታመናል በዚህ ጊዜ ዶክተሯ ይህን አታደርግም አይባልም፡፡
ላናም ወደ ኪም ዴስክ ቀረበች እና ጎንበስ ብላ በተቆጣ ድምፅ “እኔ ሌላ ቀጠሮ መያዝ ብፈልግ እነግርሽ አልነበር እንዴ?” ብላ ጠየቀቻት፡፡
ኪምም በላና ምላሽ በጣም ደንግጣ ግራ ተጋባች፡፡ “ምናልባት የሐኪሟ ደምበኞች ሳይናገሩኝ ማናገር አይጠበቅብኝ ይሆን? ብላም አሰበች እኛ
“ይቅርታ ሚስስ ግሬይ እኔ ያሰብኩት...” አለቻት፡፡
ላናም በጣም ተናድዳ ወደ ዴስኩ ሄደችና ኪም ላይ አይኗን አጉረጥርጣ
“እኔ ቀጠሮ ስፈልግ እጠይቅሻለሁ። እንዲያውም ከዚህ በኋላ እዚህ አልመጣም” ብላት እየተቆናጠረች በሩን በሀይል ዘግታ ከእንግዳ መቀበያው
ክፍል ወጣች፡፡
የበሩን በሀይል መዘጋትን የሰማችው ኒኪም ከቢሮዋ ወጥታ የእንግዳ
መቀበያ ክፍሉ ውስጥ ስትገባ ረዳቷ ኪም ቾይን አይኗ እምባ አቅርሮ ተመለከተቻት፡፡
“ይቅርታ ዶክተር እኔ ላናን ሳላበሳጫት አልቀርም። ግን እኮ ቀጠሮ ልያዝልሽ ነው እንጂ ሌላ ምንም ነገር አላልኳትም፡፡”
“አይዞሽ እሷ ሁሌም እንደዚህ ናት” ብላ ኒኪ አፅናናቻት።
“ግን እኮ ሁለተኛ እዚህ አልመጣም ብላለች። ይቅርታ ሥራሽን አበላሽሁብሽ መሰለኝ” ብላ ኪም ቾይ ማልቀስ ጀመረች፡፡
“ኧረ አታልቅሺ፡፡ ታያለሽ በሚቀጥለው ሳምንት እራሷ ትመጣለች። አሁን ተረጋጊ፡ ሌላው ደግሞ ካርተር በርክሌይ እንደመጣ አስገቢው” አለቻት፡፡
ኒኪ ወደ ቢሮዋ ተመልሳ ወንበር ላይ ቁጭ ካለች በኋላ ባሏ በሕይወት
እያለ ያለማመዳትን የትንፋሽ ልምምድ ማድረግ ጀመረች።
አየር በኃይል ወደ ውስጥ ሳቢ የሚለው የባሏ ድምፅ በውስጧ ይሰማታል፡፡ ከዚያም ወረቀቶችሽን እየነጠልሽ እንደምታስቀምጪ ሁሉ
ሃሳቦችሽንም አንድ በአንድ በየተራ እየነጠልሽ አስቀምጪያቸው።
አየር በኃይል ወደ ውስጥ ሳበች እና የመጀመሪያውን ሃሳቧን ማሰብ ጀመረች ላናን ላግዛት አልቻልኩም፡፡ እሷ ሁሌም ወጣት ሴቶችን ባየች ቁጥር ንዴቷ እየጨመረ ነው የሚመጣው፡፡ ምናልባት ወደ ሌላ ቴራፒስት ልልካት ይገባል፡፡ ቴራፒስት ብቻ ሳይሆን ሳይካትሪስትም ሳያስፈልጋት አይቀርም፡፡ ግን እንዴት ልልካት እችላለሁ?'
ለሁለተኛ ጊዜ አየር በጣም ወደ ውስጥ ሳበች እና ስለእሷ ማሰብ ጀመረች፡፡ እኔ ጥሩ ቴራፒስትም ጥሩ ሚስትም አይደለሁም፡፡ ምክንያቱም ጥሩ ሚስት ብሆን ኖሮ ለባሌ አርግዤለት ልጅ እወልድለት ነበር፡፡ እሱም ሌላ ሰው ጋር ባልሄደ ነበር፡፡' ብላ አሰበች፡፡ በመቀጠልም “አሁን ስለራሴ
ሳይሆን ስለታካሚዎቼ ነው ማሰብ የሚገባኝ እያለች ሃሳቧን ልትጀምር
ስትል ቢሮዋ ግርግዳ ላይ ያለው የተረኛ ታካሚውን መምጣት የሚገልጸው
መብራት ብልጭ ድርግም ሲል ካርተር እንደመጣ አወቀች፡፡ ከወንበሯ
ተነስታም የቢሮዋን በር ከፈተች::
ኮሪደሩ ላይ ካርተር አንድ እግሩ በጀሶ ታስሮ እና በአንደኛው ወንበር መደገፊያም ላይም ሁለት ክራንቾቹን አስቀምጧል፡፡ የቢሮውን መከፈት እንዳየም በፍጥነት ሁለቱን ክራንቾቹን በግራና በቀኝ በኩል እየተደገፈ ወደ ቢሮው ውስጥ ገባ፡፡ ኒኪ በሩን ዘግታ ካርተር ወንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ ምን ሆነህ ነው?” ብላ አስባለት ጠየቀችው፡፡
ፊቱ ላይ ላቡ ችፍ ብሎ ጠብታዎች ግንባሩ ላይ ሠርቷል፡፡ ጥርሱም
እየተንቀጫቀጨ ነው።
“በጥይት መተውኝ ነው!” አላት እና በፍርሃት ዓይን ያያት ጀመር፡፡
“በእግዚአብሔር ስም ማን ነው የመታህ? መቼ ነው ይኼ ነገር የተከሰተው?”
“ምናልባት አላማርኳቸው ይሆናል፡፡ ግን እነዚያ ሁሌም ስነግርሽ የነበሩት የሜክሲኮ ወሮበሎች ናቸው፡፡ ከዚህ ቀደም ቤቴ ገብተው የማስፈራሪያ ነገር መኝታ ቤቴ ውስጥ አስቀምጠው ነበር፡፡”
“ይህንን ደግሞ ፖሊሶች ጋር አመልክቼ ነበር፡፡ እነርሱ ግን እኔ ፈጥሬ የተናገርኩት ይመስል አላመኑኝም” አላት፡፡
ኒኪ ይህንን ስትሰማ ደነገጠች፡፡ ምክንያቱም እሷ ቤትም የሆነ ሰው
ከመኝታ ቤቷ ውስጥ የሚገኘውን የእሷና የባሏን የሠርግ ፎቶ እንደተወሰደባት ለፖሊሶች ብትነግርም እነርሱ ግን ችላ ያሉትን ነገር አስታወሰች፡፡
“እነርሱ እንደዚህ ቢያስቡም አያገባኝም፡፡ እናታቸውን... እኔ እውነታውን በደንብ ነው የማውቀው፡፡ በጥይት የተመታሁት ባለፈው ቅዳሜ ከክለብ ስወጣ ሌሊት ላይ ነው፡፡ በግምት ከሌሊቱ 7፡30 ላይ፡፡ ምናልባትም ይከታተሉን ስለነበር ያለሁበትን ቦታ አውቀውታል፡፡ እኔ ከክለቡ ወጥቼ መኪናዬን ፓርክ ያደረገው ሰው መኪናዬን እስኪያመጣልኝ ድረስ
እየጠበቅሁት ነበር፡፡ ይኼኔም አንድ መኪና ከአጠገቤ ቆመ እና ሁለት ሰዎች
ወጡ፡፡ አንደኛው ቅልጥሜ ላይ በጥይት ከመታኝ በኋላ መኪና ውስጥ
ገብተው መሬት ላይ ጥለውኝ ሄዱ፡፡”
ካርተር የደረሰበትን ነገር በፍጥነት ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ አሁንም
የደረሰበትን ነገር እያስታወሰ ጥርሱን ሲያንቀጫቅጭ ኒኪ ተመለከተችው፡፡
“በጥይት ሲመቱህ በአካባቢው ላይ ማንም አልነበረም?” ብላ ጠየቀችው፡፡
ካርተርም ጭንቅላቱን በአሉታ ወዝውዞ “ማንም አልነበረም ብቻዬን ነበርኩኝ፡ መኪናዬን ያቆመው ልጅም መኪናዬን ካቆመበት ቦታ ሊያመጣ ሄዶ ነበር፡፡ እሱ መኪናዬን ይዞ በመጣ ጊዜ እኔ መሬት ላይ ወድቄ ደሜን እያዘራሁ ከመሆኔም በላይ ራሴንም በመሳት ላይ ነበርኩኝ”
“መልካም” አለች ኒኪ፡፡ እንደሰው የነገራትን ነገር ማመን ይኖርባታል።
ምክንያቱም እሷን ለማሳመን ብሎ እግሩን በጀሶ እንደማያጅል ይገባታል፡፡
ምናልባት እንኳን የነገራት ነገር ውሽት ቢሆን እንኳን የራሱን ቅልጥም
በሽጉጥ መትቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ይህንን ለምን ያደርጋል? አትኩሮት
ፍለጋ ነው? ካርተር ደግሞ በዚህ መልኩ በሽታው ብሶበታል ብላ ኒኪ አታምንም፡፡ ምክንያቱም የባንክ ሥራውን በአግባቡ እየሰራ መሆኑን ታውቃለች
ስለሜክሲካኖቹ የወሮበሎች ቡድን በየጊዜው የሚያወራትን ነገር
ተጨባጭነት ባለው ምክንያት ሳያረጋግጥላት በጥይት ቅልጥሙን መቱት የሚለውን
👍2
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጋሻዬነህ ጌታነህ ይባላል» ብላ ጸጥ አለች። ከወዲህም ከወዲያም ከጣራውም ከወለሉም ላይ ድምፅ ስደት ገባ።
ከማን የተወለደ? የመቼው? የት የነበረ? ብላ የተሰደደውን ድምፅ መለሰችው:: ነገሩ በመፋፋሙና ጥያቄው በመድራቱ የመጣው ይምጣ ብዩ ዐይኔን ጨፍኜ ገባሁ፡፡
ምንም ሳልናር ተቀመጥኩ፡፡ ጋሻይነህ እናቴ እግሮች መካከል ቆሟል።
የውብነሽ ከእናቴ ፊት ለፊት ቆማ የአቤቱታ መልስ የሚጠባበቅ ድኃ መስላለች።እናቴ ዘወር ብላ ካየችኝ በኋላ ለዛ ባጣ ፈገግታ ገረመመችኝ፡፡ «የጌታነህማ ልጅ ከሆነ እሱው ራሱ ይናገር፣ ይኸው መጣ! አንቺ ምን ታጎበጉቢያለሽ» አለችና ዐይኖቿን ወደ ጋሻዬነህ መለሰቻቸው:: አቀረቀርኩ፡፡ ከንፈሮቼ ተጣበቁ፡፡
ያመጣኸውን ብታመጣ በደስታ እቀበልልሃለሁ፣ እፈጽምልሃለሁ ብለሽ
የአቦን ስም ጠርተሽ ምለሻል:: አሁን ወዲያ ወዲህ እንዳትይ! በዚህ ወጥቶ በዚያ ወርዶ ብሎ ነገር የለም፡፡ ታሪኩንና ሁኔታን ሁሉ ቀስ በቀስ ነገና ከነገ ወዲያ
እንዘረዝርልሻለን፡፡ አሁን ግን ምንም ምንም ሳትይ ይህን የአተር ክክ የመሰለ ልጅ ደስ ብሎሽ ተቀበይን፡፡ የሚያኮራና የሚያስደስት ነው:: ከዛሬ ስድስት ዓመት
በፊት የተወለደ የጌታነህ ልጅ ነው» ብላ በሙሉ ልብ ተዝናንታ ተቀመጠች፡፡
ከተሽከምኩት የሐሳብ ቀንበር ላይ ትንሽ ተጎርዶ ወደቀ፡፡ ደቂቃዎች ተውዘገዘጉ፡፡
እናቴ በሐሳብ ላይ እንዳለች ጋሻዬነህ ከእግሮቿ መኻል ሹልክ ብሎ ወጣና ትከሻዬን ይዞ ከጐኔ ቆመ:: ጉልህ መልስና ድንቅ ምስክርነት ነበር፡፡
እናቴ ወደ ጎን ዘወር ብላ ስታይ ሰርቀው ከሚመለከቷት ዐይኖቼ ጋር ተጋጨች፡፡ የእኔዎቹ ተሰበሩ፡፡ ፍርሃት ሳይሆን ትሕትና ሰበራቸው።
«ይሁና! አበጀህ! ደግ አረክ! ታዲያ ምን ኣለበት እንኳን ወንድ ልጅና፣ሴትም ልጅ ወልዳ ትመጣለች ! ቀና በል! የምን ማቀርቀር ነው:: ያንበሳ ግልገል
የመሰለ ልጅ ነው ያመጣኸው! እኔ እናትህ ባልምል ባልገዘትስ አንተን ልጄን
አሳፍርሃለሁ እንዴ? ደስ የሚል እንጂ የሚያሳፍር አይደለም፡፡ ያኔዬስ ቢሆን
መላውን አጥቼውና የሴት ነገር ሆኖ ተበሳጭቼ ነው እንጂ የኋላ ኋላ ሳልጠጣትና ሳያንገበግበኝ ቀርቶ መሰለህ: ሽንፍላችን ስስ ነው:: አንችልም! አንኳን አንድ ሁለትና ሦስት ቢሆንሳ? እስከ ዛሬ ድረስ ደብቀሽኝ በመኖርሀ ግን ቀስ ብለን እንወቃቀስበታለን» ብላ ጋሻዬነህን ወስዳ አገላብጣ ሳመችው። የደስታና የርኅራኄ እንባ ዐይኖቿ ላይ ተንቀዋለለ።
ጨምደድ ባለው ፊቷ ላይ የኃፍረትና የጸጸት ስስ ፈገግታ ታየ። አምጣ አምጣ እንደ ተገላገለች ነፍሰ ጡር እኔም የሐሳቤን እትብት አስቆርጡ አፎይ
አልኩ፡፡
«አቤት እኔ! ይኸስ እውነትም እልል በይ የሚያሰኝ ነው፡፡ በል አንተ ትልቁ ልጅ
ደግሞ ሳመኝ፡፡ ምንስ ቢሆን ከጥጃይቱ በፊት እናቲቱ” ይሉ የለ፡፡ ከዚህ የበለጠ
ዓለም የት ይገኛል» ብላ ከመናገሯ እመር ብዬ ሄጀ ተሳሳምን፡፡ የውብነሽ በደስታ
ተፍነከነከች፡፡ ደሜ የፈንጠዚያ ግልቢያ ጋለበ። ዐይኖቼ በእናቴ በኩል የሚደረገውን የተስፋና የጉጉት ውጤት አፍጥጠው ተመለከቱ። በእናቴ የፍቅር
ሚዛን ላይ የዱሮው ጌታነህ ለመሆን ተቃረብኩ፡፡ ወንዙን ላደነቀ ምንጩን
ማሳየት አስፈላጊ በመሆኑ የጋሻዬነህን ምንጭ ማሳየት አስፈላጊ ነው፡፡
ተመስገን! ተመስገን! ክብርህ ይስፋ! እንኳን ለዚህ ያበቃኸኝ! ኖረህ ኖረህ ይህን የመሰለ ልጅ ይዘህልኝ ስትመጣ ምን ከፍቶኝ! አቦዬም ስለታቸውን አገኙ፡፡ ትንሽም ቅር የሚለኝ እንደ ወንድሞችህና እኅቶችህ ወግ ማረግ...አረ ምን አባቱ! ይሁን! ዞሮ ዞሮ ለዚሁ አይደል?» አለችና ከሕሊናዋ ጋር ለመግባባት አስተያየቷን መለወጥ ሞከረች፡፡ እንደ ወንድሞቼና እህቶቼ እንድሆንላት ስትመኝ የነበረው ምኞቷና ፍላጎቷ ሁሉ በዚህ ባልጠበቀችው ሁኔታና ኢጋጣሚ ከሰመ፡፡
«ደስ አለሽ? እኛማ በጣም ፈርተንና ተጨንቀን ነበር፡፡ እንዲህ በቀላሉ
ይቀናናል፣ እንዲህ ባለ ሁኔታ ይሳካልናል ብለን በፍፁም አላሰብንም ነበር?» ብላ
የእናቴን ኃይለኛነትና ትፈሪነት ለማስገንዘብ ሞከረች፡፡ እግረ መንገዷንም የእናቴ ስሜት ወደ እኛ እንዲያዘነብል ማጎሳመሷ ነበር፡፡
«እስኪ ተይኝ ልጀ! የዛሬዋን ደስታዩን ዝግ ብለን ልባችንን አስፍተን እንጫወታለን፡፡ ጌታነህ እንበሳ ከነነፍሱ ይዞልኝ መጥቷል» ካለች በኋላ ጋሻዬነህን
ለየውብነሽ ሰጥታ ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ሄደች። እኔና የውብነሽ በደስታ
ተቃቅፈን ተሳሳምን። ጋሻዬነህንም ለሁለት ኣንሥተን «አንተ ዕድለኛ» ብለን
በየአቅጣጫችን ያለውን ጉንጩን ስመን ወደየነበርንበት ቦታ ተመልሰን
ተቀመጥን። ሰው በደስታ ይፈነዳ ሲሆን ያለጥርጥር እፈነዳ ነበር። አንዲት
ሠራተኛ የእጅ ውሃ አምጥታ እንዳስታጠበችን እናታችን ገባች። ይኽነዩ ነበር የቀድሞው የየወዲያነሽ ሕይወት ትዝ ያለኝና መንፈሴ ስለ ባለቤቴ
የተሠቃየው:: በሌሎች ሁለት ሠራተኞች ደግሞ ምግብና መጠጥ በየተራ ቀረበ።
«የቤታችንን የሲሳይ ርጥበት አሳምሬ ስለማውቀው በቀረበው መስተንግዶ
አልተደነቅሁም፡፡
እህል ብቻ ሳይሆን የደስታ እንክብክብ ጎረስኩ፡፡ ባልገመትኩት አኳኋን ወኔና ብርታት አካበትኩ፡፡ አዲስ የኑሮ ተስፋ ከፊት ለፊቴ ተዘረጋ፡፡ አጋጣሚና
ድል የሚባለው ይኸ ይሆን? እስከ ማለት ደረስኩ፡፡ እናቴ ወደ እፏ ከላከችው
ይልቅ ለእኔና ለጋሻዬነህ ያጎረሰችን ይበልጣል። የጣቶቿ ጫፎች ከንፈሮቼን
እየነኩ ሲመለሱ የእናትነቷን ውድ ፍቅር እያቀበሉኝ ተመለሱ።
ጋሻዬነህ አካባቢውን ስለተለማመደው ያ በግርታ መጦ የነበረው ፊቱ እጥፍ ፈገግታ አንዠረገገ። ገበታው ከፍ ኣለ። የአዲሱ ግንኙነት ማዕድ ግን በሰፊው ቀጠለ። እናቴ ብርጭቆዋ ውስጥ የነበረችውን ጠላዋን ተጎንጭታ
ጉሮሮዋን ካራሰች በኋላ እናንተ ግን ምስጥ ናችሁ፣ ልባችሁ አይገኝም፡፡
የገረመኝ ደግሞ ሆን ብላችሁ አባታችሁ በሌለበት ቀን መምጣታችሁ ነው::
የናንተን ብልጠት ማን ያገኘዋል» አለችና ተንኮል የሌለበት ሣቅ ሣቀች፡፡
«ከአባታችን ይልቅ አንቺን በመጀመሪያ ብንጠይቅና ብናሸንፍ፣ አንቺ
ካየሽው በኋላ የምትይንን ለማወቅ ብለን ነው:: በተለይ የዛሬዋን ቀን ጠብቀን
የመጣነው» ብላ የውብነሽ በጠላዋ ውስጥ የምትታየውን የገዛ ፊቷን ምስል
ለማየት አንገቷን ወደ ብርጭቆው አሰገገችው።
«ኧረ ለመሆኑ አንቺ ይኸ ልጅ መወለዱን የሰማሽውና ያወቅሽው መቼ ነው?» ብላ መገረሟን በሚገልጽ ስሜት ጠየቀቻት። የውብነሽ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ «አጅሬ መች እንዲህ የዋዛ ሰው ነውና! እኔም ያየሁት አሁን በቅርቡ ነው:: ያም ሆነ ይህ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ የቀረውን ተይኝ» በማለት ወቀሳ የቦረቦረው ድጋፍ አደረገችልኝ። የጋሻዬነህ እናት ማንነት እና ስሟ ተጠቅሶ ባለመነገሩ በውስጤ የሚፈራገጠውን ጭንቀቴን አጠቃልዬ አልገደልኩም፡፡
«ኧረ ለመሆኑ እናቱ ማን ትባላለች? የማን ልጅ ትሆን? አልነገራችሁኝም እኮ?» ብላ ሁለታችንንም. በየተራ አየችን፡፡ እኔና የውብነሽ ተፋጠጥን! ይህን ለጊዜው በምሥራችነት የማይነገር ታላቅ ጉዳይ ማን ያርዳ?
የውብነሽ መልስ ለመስጠት አልዘገየችም፡፡ «የእናቱ ጉዳይ ግልጽም
??ስውርም ነው:: ከዚህ ቤት ይጀምርና ወደ ሌላ ሰፊ ሥፍራ ይጓዛል። ዳቦውን
ገምጦ ምጣዱን መጥላት አይገባም፡፡ የዚህ ልጅ እናት አንቺ እንደምትመኘው
የማንም ትልቅ ሰው ልጅ አይደለችም፡፡ በደፈናው የሰው ልጅ ነች፡፡ እስከ አሁን
ድረስ ፈርተናል ፣ተጨንቀናል፣ ከእንግዲህ ግን በቃ! የዚህ ልጅ እናት የመከራ
እሳት የለበለባት፡ የሥቃይ ቀንበር የተጫናት፣ የሰው ፊት እንደ እሳት ነበልባል
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጋሻዬነህ ጌታነህ ይባላል» ብላ ጸጥ አለች። ከወዲህም ከወዲያም ከጣራውም ከወለሉም ላይ ድምፅ ስደት ገባ።
ከማን የተወለደ? የመቼው? የት የነበረ? ብላ የተሰደደውን ድምፅ መለሰችው:: ነገሩ በመፋፋሙና ጥያቄው በመድራቱ የመጣው ይምጣ ብዩ ዐይኔን ጨፍኜ ገባሁ፡፡
ምንም ሳልናር ተቀመጥኩ፡፡ ጋሻይነህ እናቴ እግሮች መካከል ቆሟል።
የውብነሽ ከእናቴ ፊት ለፊት ቆማ የአቤቱታ መልስ የሚጠባበቅ ድኃ መስላለች።እናቴ ዘወር ብላ ካየችኝ በኋላ ለዛ ባጣ ፈገግታ ገረመመችኝ፡፡ «የጌታነህማ ልጅ ከሆነ እሱው ራሱ ይናገር፣ ይኸው መጣ! አንቺ ምን ታጎበጉቢያለሽ» አለችና ዐይኖቿን ወደ ጋሻዬነህ መለሰቻቸው:: አቀረቀርኩ፡፡ ከንፈሮቼ ተጣበቁ፡፡
ያመጣኸውን ብታመጣ በደስታ እቀበልልሃለሁ፣ እፈጽምልሃለሁ ብለሽ
የአቦን ስም ጠርተሽ ምለሻል:: አሁን ወዲያ ወዲህ እንዳትይ! በዚህ ወጥቶ በዚያ ወርዶ ብሎ ነገር የለም፡፡ ታሪኩንና ሁኔታን ሁሉ ቀስ በቀስ ነገና ከነገ ወዲያ
እንዘረዝርልሻለን፡፡ አሁን ግን ምንም ምንም ሳትይ ይህን የአተር ክክ የመሰለ ልጅ ደስ ብሎሽ ተቀበይን፡፡ የሚያኮራና የሚያስደስት ነው:: ከዛሬ ስድስት ዓመት
በፊት የተወለደ የጌታነህ ልጅ ነው» ብላ በሙሉ ልብ ተዝናንታ ተቀመጠች፡፡
ከተሽከምኩት የሐሳብ ቀንበር ላይ ትንሽ ተጎርዶ ወደቀ፡፡ ደቂቃዎች ተውዘገዘጉ፡፡
እናቴ በሐሳብ ላይ እንዳለች ጋሻዬነህ ከእግሮቿ መኻል ሹልክ ብሎ ወጣና ትከሻዬን ይዞ ከጐኔ ቆመ:: ጉልህ መልስና ድንቅ ምስክርነት ነበር፡፡
እናቴ ወደ ጎን ዘወር ብላ ስታይ ሰርቀው ከሚመለከቷት ዐይኖቼ ጋር ተጋጨች፡፡ የእኔዎቹ ተሰበሩ፡፡ ፍርሃት ሳይሆን ትሕትና ሰበራቸው።
«ይሁና! አበጀህ! ደግ አረክ! ታዲያ ምን ኣለበት እንኳን ወንድ ልጅና፣ሴትም ልጅ ወልዳ ትመጣለች ! ቀና በል! የምን ማቀርቀር ነው:: ያንበሳ ግልገል
የመሰለ ልጅ ነው ያመጣኸው! እኔ እናትህ ባልምል ባልገዘትስ አንተን ልጄን
አሳፍርሃለሁ እንዴ? ደስ የሚል እንጂ የሚያሳፍር አይደለም፡፡ ያኔዬስ ቢሆን
መላውን አጥቼውና የሴት ነገር ሆኖ ተበሳጭቼ ነው እንጂ የኋላ ኋላ ሳልጠጣትና ሳያንገበግበኝ ቀርቶ መሰለህ: ሽንፍላችን ስስ ነው:: አንችልም! አንኳን አንድ ሁለትና ሦስት ቢሆንሳ? እስከ ዛሬ ድረስ ደብቀሽኝ በመኖርሀ ግን ቀስ ብለን እንወቃቀስበታለን» ብላ ጋሻዬነህን ወስዳ አገላብጣ ሳመችው። የደስታና የርኅራኄ እንባ ዐይኖቿ ላይ ተንቀዋለለ።
ጨምደድ ባለው ፊቷ ላይ የኃፍረትና የጸጸት ስስ ፈገግታ ታየ። አምጣ አምጣ እንደ ተገላገለች ነፍሰ ጡር እኔም የሐሳቤን እትብት አስቆርጡ አፎይ
አልኩ፡፡
«አቤት እኔ! ይኸስ እውነትም እልል በይ የሚያሰኝ ነው፡፡ በል አንተ ትልቁ ልጅ
ደግሞ ሳመኝ፡፡ ምንስ ቢሆን ከጥጃይቱ በፊት እናቲቱ” ይሉ የለ፡፡ ከዚህ የበለጠ
ዓለም የት ይገኛል» ብላ ከመናገሯ እመር ብዬ ሄጀ ተሳሳምን፡፡ የውብነሽ በደስታ
ተፍነከነከች፡፡ ደሜ የፈንጠዚያ ግልቢያ ጋለበ። ዐይኖቼ በእናቴ በኩል የሚደረገውን የተስፋና የጉጉት ውጤት አፍጥጠው ተመለከቱ። በእናቴ የፍቅር
ሚዛን ላይ የዱሮው ጌታነህ ለመሆን ተቃረብኩ፡፡ ወንዙን ላደነቀ ምንጩን
ማሳየት አስፈላጊ በመሆኑ የጋሻዬነህን ምንጭ ማሳየት አስፈላጊ ነው፡፡
ተመስገን! ተመስገን! ክብርህ ይስፋ! እንኳን ለዚህ ያበቃኸኝ! ኖረህ ኖረህ ይህን የመሰለ ልጅ ይዘህልኝ ስትመጣ ምን ከፍቶኝ! አቦዬም ስለታቸውን አገኙ፡፡ ትንሽም ቅር የሚለኝ እንደ ወንድሞችህና እኅቶችህ ወግ ማረግ...አረ ምን አባቱ! ይሁን! ዞሮ ዞሮ ለዚሁ አይደል?» አለችና ከሕሊናዋ ጋር ለመግባባት አስተያየቷን መለወጥ ሞከረች፡፡ እንደ ወንድሞቼና እህቶቼ እንድሆንላት ስትመኝ የነበረው ምኞቷና ፍላጎቷ ሁሉ በዚህ ባልጠበቀችው ሁኔታና ኢጋጣሚ ከሰመ፡፡
«ደስ አለሽ? እኛማ በጣም ፈርተንና ተጨንቀን ነበር፡፡ እንዲህ በቀላሉ
ይቀናናል፣ እንዲህ ባለ ሁኔታ ይሳካልናል ብለን በፍፁም አላሰብንም ነበር?» ብላ
የእናቴን ኃይለኛነትና ትፈሪነት ለማስገንዘብ ሞከረች፡፡ እግረ መንገዷንም የእናቴ ስሜት ወደ እኛ እንዲያዘነብል ማጎሳመሷ ነበር፡፡
«እስኪ ተይኝ ልጀ! የዛሬዋን ደስታዩን ዝግ ብለን ልባችንን አስፍተን እንጫወታለን፡፡ ጌታነህ እንበሳ ከነነፍሱ ይዞልኝ መጥቷል» ካለች በኋላ ጋሻዬነህን
ለየውብነሽ ሰጥታ ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ሄደች። እኔና የውብነሽ በደስታ
ተቃቅፈን ተሳሳምን። ጋሻዬነህንም ለሁለት ኣንሥተን «አንተ ዕድለኛ» ብለን
በየአቅጣጫችን ያለውን ጉንጩን ስመን ወደየነበርንበት ቦታ ተመልሰን
ተቀመጥን። ሰው በደስታ ይፈነዳ ሲሆን ያለጥርጥር እፈነዳ ነበር። አንዲት
ሠራተኛ የእጅ ውሃ አምጥታ እንዳስታጠበችን እናታችን ገባች። ይኽነዩ ነበር የቀድሞው የየወዲያነሽ ሕይወት ትዝ ያለኝና መንፈሴ ስለ ባለቤቴ
የተሠቃየው:: በሌሎች ሁለት ሠራተኞች ደግሞ ምግብና መጠጥ በየተራ ቀረበ።
«የቤታችንን የሲሳይ ርጥበት አሳምሬ ስለማውቀው በቀረበው መስተንግዶ
አልተደነቅሁም፡፡
እህል ብቻ ሳይሆን የደስታ እንክብክብ ጎረስኩ፡፡ ባልገመትኩት አኳኋን ወኔና ብርታት አካበትኩ፡፡ አዲስ የኑሮ ተስፋ ከፊት ለፊቴ ተዘረጋ፡፡ አጋጣሚና
ድል የሚባለው ይኸ ይሆን? እስከ ማለት ደረስኩ፡፡ እናቴ ወደ እፏ ከላከችው
ይልቅ ለእኔና ለጋሻዬነህ ያጎረሰችን ይበልጣል። የጣቶቿ ጫፎች ከንፈሮቼን
እየነኩ ሲመለሱ የእናትነቷን ውድ ፍቅር እያቀበሉኝ ተመለሱ።
ጋሻዬነህ አካባቢውን ስለተለማመደው ያ በግርታ መጦ የነበረው ፊቱ እጥፍ ፈገግታ አንዠረገገ። ገበታው ከፍ ኣለ። የአዲሱ ግንኙነት ማዕድ ግን በሰፊው ቀጠለ። እናቴ ብርጭቆዋ ውስጥ የነበረችውን ጠላዋን ተጎንጭታ
ጉሮሮዋን ካራሰች በኋላ እናንተ ግን ምስጥ ናችሁ፣ ልባችሁ አይገኝም፡፡
የገረመኝ ደግሞ ሆን ብላችሁ አባታችሁ በሌለበት ቀን መምጣታችሁ ነው::
የናንተን ብልጠት ማን ያገኘዋል» አለችና ተንኮል የሌለበት ሣቅ ሣቀች፡፡
«ከአባታችን ይልቅ አንቺን በመጀመሪያ ብንጠይቅና ብናሸንፍ፣ አንቺ
ካየሽው በኋላ የምትይንን ለማወቅ ብለን ነው:: በተለይ የዛሬዋን ቀን ጠብቀን
የመጣነው» ብላ የውብነሽ በጠላዋ ውስጥ የምትታየውን የገዛ ፊቷን ምስል
ለማየት አንገቷን ወደ ብርጭቆው አሰገገችው።
«ኧረ ለመሆኑ አንቺ ይኸ ልጅ መወለዱን የሰማሽውና ያወቅሽው መቼ ነው?» ብላ መገረሟን በሚገልጽ ስሜት ጠየቀቻት። የውብነሽ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ «አጅሬ መች እንዲህ የዋዛ ሰው ነውና! እኔም ያየሁት አሁን በቅርቡ ነው:: ያም ሆነ ይህ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ የቀረውን ተይኝ» በማለት ወቀሳ የቦረቦረው ድጋፍ አደረገችልኝ። የጋሻዬነህ እናት ማንነት እና ስሟ ተጠቅሶ ባለመነገሩ በውስጤ የሚፈራገጠውን ጭንቀቴን አጠቃልዬ አልገደልኩም፡፡
«ኧረ ለመሆኑ እናቱ ማን ትባላለች? የማን ልጅ ትሆን? አልነገራችሁኝም እኮ?» ብላ ሁለታችንንም. በየተራ አየችን፡፡ እኔና የውብነሽ ተፋጠጥን! ይህን ለጊዜው በምሥራችነት የማይነገር ታላቅ ጉዳይ ማን ያርዳ?
የውብነሽ መልስ ለመስጠት አልዘገየችም፡፡ «የእናቱ ጉዳይ ግልጽም
??ስውርም ነው:: ከዚህ ቤት ይጀምርና ወደ ሌላ ሰፊ ሥፍራ ይጓዛል። ዳቦውን
ገምጦ ምጣዱን መጥላት አይገባም፡፡ የዚህ ልጅ እናት አንቺ እንደምትመኘው
የማንም ትልቅ ሰው ልጅ አይደለችም፡፡ በደፈናው የሰው ልጅ ነች፡፡ እስከ አሁን
ድረስ ፈርተናል ፣ተጨንቀናል፣ ከእንግዲህ ግን በቃ! የዚህ ልጅ እናት የመከራ
እሳት የለበለባት፡ የሥቃይ ቀንበር የተጫናት፣ የሰው ፊት እንደ እሳት ነበልባል
👍3👏1
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....የዓመቱ መጨረሻ ስለሆነ ትምህርት ቤቷ የወላጆች ቀን በአሏን በማክበር ላይ ትገኛለች። ዘይኑ እንደተለመደው በደረጃ ከክፍሏ አንደኛ ወጥታ ወደ ስድስተኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ለአምስት አመታት ከጓደኞቿ ጋር የቦረቀችበትን ትምርት ቤት የመሰነባበቻዋ ዕለት ነበር። ሽልማቷን ብትቀበልም አይኖችዋ እምባ መቋጠራቸውን አልተዉም፡፡ እናቷም ረዳቻት።አብራት አለቀሰች፡፡ የጎበዝ ልጅ እናት መሆን እንዴት ደስ ይላል? ግራ
ቀኟ ለተቀመጡት ወላጆች የሷ ልጅ መሆኗን በኩራት ገለፀችላቸው::
“ጎሽ የተባረከች ልጅ እንጀራ ይውጣላት። ሴት ልጅ እንደዚህ ስትሆን መታደል ነው” በማለት አደነቁላት፡፡
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ከመስተንግዶው ጋር መሳ ለመሳ ሲጓዝ ቆየ።ዘይኑ የትምህርት ቤት ሰርተፊኬቷን አወጣች። መጪው መስከረም ነው፡፡ የመስከረም ወር ሳሩ ቅጠሉ ለምልሞ የሚታይበት አዲሱ ዓመት አዲስ
ተስፋን ይዞ የሚመጣበት የዘመን መለወጫ በመሆኑ ወዳድ
ዘመዱ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ የሚባባልባት ተወዳጅ ወር ናት፡፡ መስከረም "በአበባ አየሽወይ" የህፃናት ጣፋጭ ጣዕመ ዜማ የምታሽበርቅ ወር....
እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ፣
በአበቦች መሀል አሽብርቀሽ..
እየተባለች የምትወደስ የአዲሱ አመት መክፈቻ በር ዘይኑም ከሰፈሯ ልጆች ጋር በአዲስ ልብስ አምራና ተውባ "አበባ አየሽ ወይን" ትጫወታለች።
ባልንጀሮቼ ቁሙ በተራ፣
እንጨት ሰብሬ ቤት እስክሰራ፣
እንኳን ቤትና የለኝም አጥር፣
ከደጅ አድራለሁ ኮከብ ስቆጥር።
ኮከብ ቆጥሬ ስገባ ቤቴ፣
ትቆጣኛለች እንጀራ እናቴ...
በአንድ አውራጅ እየተቀባበሉ የሚፈነድቁባት የመስከረም ወር መጣች፡፡ ዘይኑ ይቺን በናፍቆት የምትጠብቃት "የአበባ አየሽወይ" በዓልን ሳታከብር ወደ ወንድሟ እንድትሄድ እናቷ ስለወሰነች የትምህር ቤት ጣጣዋን
ሁሉ ጨርሳ የአዲስ አበባ ተጓዥ መንገደኛ ሆነች፡፡ የምትነሳበት ቀን
ተቆርጦ ወንድሟ እንዲጠብቃት ተነገረው። በዚሁ መሠረት አቶ አለሙ ይዘዋት ሊሄዱ ተነሱ... በዚህ ጊዜ እናትና ልጅ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው ተላቀሱ፡፡ ልጀቿን ወደ አዲስ አበባ ሸኝታ የጨረሰችው እናት ብቻዋን ልትቀር እጅግ የምታፈቅራት ሴት ልጅዋን መሸኘት ግዴታዋን ሆነ።
"በሄድሽበት ሁሉ እንደ ማር እንደ ወተት ጣፍጪ። አንድ ቀን እንኳ
እንደ ትንሽ ልጅ ተሳስታ ሰው ሳታስቀይም ሁሉን እሺ እንዳለች ለሁሉ እንደታዘዘች" ሊሸሿት የመጡት በሙሉ አድናቆታቸውን እየገለፁ እሷንም እንደ ወንድሟ መረቋት፡፡
እናት ከዐይኖችዋ ያለማቋረጥ የሚፈስ እንባዋን በነጠላዋ ጫፍ ቶሎ ቶሎ እያበሰች ልትሸኛቸው አብራ ተነሳች። አውቶቡሱ ረጅም ጡሩምባውን አሰማ፡፡ "ፑም! ጥም! ፓም! ፓም!እረም!.. እረም!” አለና በጢስ ማውጫው በኩል ጥቁር ጥጥ የመሰለ ወፍራም ጢስ ትጉልል አድርጎ
አስወጣ፡፡ ያንን የመኪናውን አሸባሪ ተዘጋጁ! ተዘጋጁ! የሚለውን ድምፅ ስትሰማ እንደ አዲስ ልቧ ሽብር ሽብር አለባት። አንጀቷ ተላወሰ፡፡ጣፋጫ ትንሽዋ ዘይኑ ልትሄድ ነው፡፡
በሉ እንግዲህ ጋሼ ዓለሙ እሱ ፈጣሪ ይከተላችሁ በደህና ግቡ...”ልጇን እቅፍ አድርጋ ለመጨረሻ ጊዜ ስማ ተሰናበተቻቸው። አቶ ዓለሙ
በቶሎ ብለው ዘይኑን እጅዋን ያዙና ወደ መኪናው ገቡ፡፡ ዘይኑም እንባዋን እያፈሰሰች በመስታወቱ ፊቷን ብቅ አደረገችና እናቷን አይን አይኗን አየቻት። ከዚያም ትንሿን እጅዋን አውለበለበችላት...
ቻዎ! ቻዎ! ባይ! ባይ! እማምዬ..” መኪናው ተንቀሳቀሰ፡፡ እናት ወገቧ
እየተንቀጠቀጠ እግሯ እየተብረከረከ ስለተቸገረች በቆመችበት ቦታ ላይ ቁጢጥ አለች።
"ምነው አመመሽ እንዴ?" አሉ ጎረቤቷ ወይዘሮ ተዋበች። መልስ አልሰጠቻቸውም፡፡ መናገር አቃታት።
"በይ በርቺ ከንግዲህ አንቺም ወደዚያው ወደነሱ መጠቃለልሽ አይቀርም፡፡ እስከዚያው ድረስ ግን ብቸኝነቱን ጠንከር ብለሽ መቋቋም አለብሽ አውቶቡሱ እየተመዘገዘገ ጉዞውን ወደ ፊት ቀጠለ... ዳገት ቁልቁለቱን
ጋራ ሽንተረሩን ጫካና ሜዳውን እያቆራረጠ ወደ ፊት ተወነጨፈ
የባሌ ደን መቼም ለጉድ ነው፡፡ ዘይኑ የደኑን ውበት እያደነቀች አሻግራ የምታያቸው ዛፎች ሁሉ እየተነሱ የሚፈርጡ እየመሰላት
እየተገረመች ሰብስቤ ዋሻ ደረሱ፡፡ ሰብስቤ ዋሻን ቁልቁል ስትመለከተው ፍርሀት ፍርሀት አላት። እዚያ ግድም ሰማይ ተገምሶ የወደቀ ይመስላል። ከላይ ወደ ታች የሆነ ነገር ቢወረወር መሬት ለመድረስ ሳምንት የሚፈጅበት ይመስላል። መኪናው ወደ ፊት ነጎደ
"ሙጨዮ በረከቴ ኢጀ በዳ ሲንላለን! የተባረክሽ ልጅ ክፉ ዐይን አይይሽ.."እያሉ የሚመርቋት የሚወዷት ጎረቤቶቿ ትዝታ ከእናቷ ትዝታ ጋር በዐይኖቿ ላይ እየተንቀዋለለ የተራራውንና የሜዳውን ግልቢያ አሻግራ
ስትመለከት እየተደነቀች ወደ አዲስ አበባ ወደ ወንድም ጋሻዋ ከነፈች…..መኪናው በየመንገዱ ላይ እየቆመ ሸንኮራ አገዳ፣ ብርቱካን፣ ሙዝ፣ፓፓያ ለመሽጥ የሚሮጡ ልጆችን እያስተናገደ ተሳፋሪው በመስታወቱ አንገቱን ብቅ እያደረገ እየገዛ እየተቋደሰ ጉዞው ቀጠለ...
"ይህችን! ይህችን ጣፋጭ ብርቱካን! መንደሪን!. . ሙዝ አለ ሙዝ! አለ ሙዝ! ሽንኮራ ጣፋጭ ሸንኮራ አገዲ!" ሁሉም የሚሸጡትን እያወደሱ ከጣዕሙ የበለጠ በቃላት እያጣፈጡ ለመሸጥ ይሯሯጣሉ። መኪናው
በዚህ ሁኔታ ሲጓዝ ውሎ ሻሽመኔ ከተማ ደረሰ፡፡ አቶ አለሙ ዘይኑን
ይዘው ምሳ ለመብላት ወደ ኢየሩሳሌም ሆቴል ገቡ። ሆቴሉ በተስተናጋጅ እንግዶች ተጣቧል፡፡ አስተናጋጆችም ወዲያና ወዲህ ይሯሯጣሉ።
“ሄይ! ምነው ቶሎ በል እንጂ! ለአዳር አልመጣንምኮ?!"
“ምነው ባክህ ገና እያረዳችሁ ነው እንዴ? የበሰለ ወጥ ጨልፎ ለማምጣት እስከዚህ ድረስ?!.
“ከኛ በኋላ የገባው ስንቱ ተሸኘ በናታችሁ? ስማ ወንድም! መኪና ጥሎን ይሄዳልኮ ያንተን ሩጫ ለማየት አልመጣንም " ከሁሉም የሚሰነዘራውን ወቀሳ የሚስማው አስተናጋጅ.."እሺ ጌታዬ ይደርሳል አሁኑኑ አመጣለሁ" ለዘገየበት ይቅርታ ጠይቆ ይከንፋል። ደግሞ ይሮጣል.እሺ! እሺ! ማለቱ ተመጋቢውን ከንዴቱ ትንሽ መለስ ያደርገዋል። የተባረከ አስተናጋጅ በመሆኑ እንጂ እንደ ሌሎቹ ቢሆን ኖሮ ያንን ሁሉ ወቀሳና ዘለፋ
በትዕግስት አያሳልፈውም ነበር፡፡ ደንበኛን ላበሳጩበት ደመወዝ የሚከፈላቸው የሚመስላቸውን ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ ለስድብ የሚጋበዙም ሞልተዋል፡፡ይሄኛው ግን ፍፁም የተለየ ነው፡፡ ዘይኑ የአቶ አለሙን ጉልበት ተደግፋ የተመጋቢዎቹን ሁኔታ“ የአስተናጋጆቹን ሩጫ ስትመለከት
ደስ አላት። አይታው የማታውቀው ድራማ ነበር፡፡ ዘይኑና አቶ አለሙ
ተራቸው ደርሶ አስተናጋጁ ያመጣላቸውን ምግብ ከበሉና ለስላሳቸውን ጠጥተው ጥቂት እረፍት ከወሰዱ በኋላ መኪናው ለመንቀሳቀስ ጥሩምባውን አሰማ፡፡ በጊዜ የተጠናቀቀው በፍጥነት ብድግ እያለ ሲወጣ የዘገየው ደግሞ ሁለቴና ሶስቴ ይመላለስበት የነበረውን በአንድ ጉርሻ እያጠቃ በፍአጥነት ተነሳ ፡፡ ከዚያም ጉዞው ቀጥሎ ሞጆ ከተማ ደረሱ፡፡
“እንግዲህ አዲስ አበባ ልንገባ ደርስናል ወንድም ጋሼሽን ልታገኝው ትንሽ ነው የቀረሽ፡፡ ደስ ይበልሽ!” አሏት፡፡ ዘይኑ ፊቷ ፈካ ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....የዓመቱ መጨረሻ ስለሆነ ትምህርት ቤቷ የወላጆች ቀን በአሏን በማክበር ላይ ትገኛለች። ዘይኑ እንደተለመደው በደረጃ ከክፍሏ አንደኛ ወጥታ ወደ ስድስተኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ለአምስት አመታት ከጓደኞቿ ጋር የቦረቀችበትን ትምርት ቤት የመሰነባበቻዋ ዕለት ነበር። ሽልማቷን ብትቀበልም አይኖችዋ እምባ መቋጠራቸውን አልተዉም፡፡ እናቷም ረዳቻት።አብራት አለቀሰች፡፡ የጎበዝ ልጅ እናት መሆን እንዴት ደስ ይላል? ግራ
ቀኟ ለተቀመጡት ወላጆች የሷ ልጅ መሆኗን በኩራት ገለፀችላቸው::
“ጎሽ የተባረከች ልጅ እንጀራ ይውጣላት። ሴት ልጅ እንደዚህ ስትሆን መታደል ነው” በማለት አደነቁላት፡፡
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ከመስተንግዶው ጋር መሳ ለመሳ ሲጓዝ ቆየ።ዘይኑ የትምህርት ቤት ሰርተፊኬቷን አወጣች። መጪው መስከረም ነው፡፡ የመስከረም ወር ሳሩ ቅጠሉ ለምልሞ የሚታይበት አዲሱ ዓመት አዲስ
ተስፋን ይዞ የሚመጣበት የዘመን መለወጫ በመሆኑ ወዳድ
ዘመዱ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ የሚባባልባት ተወዳጅ ወር ናት፡፡ መስከረም "በአበባ አየሽወይ" የህፃናት ጣፋጭ ጣዕመ ዜማ የምታሽበርቅ ወር....
እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ፣
በአበቦች መሀል አሽብርቀሽ..
እየተባለች የምትወደስ የአዲሱ አመት መክፈቻ በር ዘይኑም ከሰፈሯ ልጆች ጋር በአዲስ ልብስ አምራና ተውባ "አበባ አየሽ ወይን" ትጫወታለች።
ባልንጀሮቼ ቁሙ በተራ፣
እንጨት ሰብሬ ቤት እስክሰራ፣
እንኳን ቤትና የለኝም አጥር፣
ከደጅ አድራለሁ ኮከብ ስቆጥር።
ኮከብ ቆጥሬ ስገባ ቤቴ፣
ትቆጣኛለች እንጀራ እናቴ...
በአንድ አውራጅ እየተቀባበሉ የሚፈነድቁባት የመስከረም ወር መጣች፡፡ ዘይኑ ይቺን በናፍቆት የምትጠብቃት "የአበባ አየሽወይ" በዓልን ሳታከብር ወደ ወንድሟ እንድትሄድ እናቷ ስለወሰነች የትምህር ቤት ጣጣዋን
ሁሉ ጨርሳ የአዲስ አበባ ተጓዥ መንገደኛ ሆነች፡፡ የምትነሳበት ቀን
ተቆርጦ ወንድሟ እንዲጠብቃት ተነገረው። በዚሁ መሠረት አቶ አለሙ ይዘዋት ሊሄዱ ተነሱ... በዚህ ጊዜ እናትና ልጅ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው ተላቀሱ፡፡ ልጀቿን ወደ አዲስ አበባ ሸኝታ የጨረሰችው እናት ብቻዋን ልትቀር እጅግ የምታፈቅራት ሴት ልጅዋን መሸኘት ግዴታዋን ሆነ።
"በሄድሽበት ሁሉ እንደ ማር እንደ ወተት ጣፍጪ። አንድ ቀን እንኳ
እንደ ትንሽ ልጅ ተሳስታ ሰው ሳታስቀይም ሁሉን እሺ እንዳለች ለሁሉ እንደታዘዘች" ሊሸሿት የመጡት በሙሉ አድናቆታቸውን እየገለፁ እሷንም እንደ ወንድሟ መረቋት፡፡
እናት ከዐይኖችዋ ያለማቋረጥ የሚፈስ እንባዋን በነጠላዋ ጫፍ ቶሎ ቶሎ እያበሰች ልትሸኛቸው አብራ ተነሳች። አውቶቡሱ ረጅም ጡሩምባውን አሰማ፡፡ "ፑም! ጥም! ፓም! ፓም!እረም!.. እረም!” አለና በጢስ ማውጫው በኩል ጥቁር ጥጥ የመሰለ ወፍራም ጢስ ትጉልል አድርጎ
አስወጣ፡፡ ያንን የመኪናውን አሸባሪ ተዘጋጁ! ተዘጋጁ! የሚለውን ድምፅ ስትሰማ እንደ አዲስ ልቧ ሽብር ሽብር አለባት። አንጀቷ ተላወሰ፡፡ጣፋጫ ትንሽዋ ዘይኑ ልትሄድ ነው፡፡
በሉ እንግዲህ ጋሼ ዓለሙ እሱ ፈጣሪ ይከተላችሁ በደህና ግቡ...”ልጇን እቅፍ አድርጋ ለመጨረሻ ጊዜ ስማ ተሰናበተቻቸው። አቶ ዓለሙ
በቶሎ ብለው ዘይኑን እጅዋን ያዙና ወደ መኪናው ገቡ፡፡ ዘይኑም እንባዋን እያፈሰሰች በመስታወቱ ፊቷን ብቅ አደረገችና እናቷን አይን አይኗን አየቻት። ከዚያም ትንሿን እጅዋን አውለበለበችላት...
ቻዎ! ቻዎ! ባይ! ባይ! እማምዬ..” መኪናው ተንቀሳቀሰ፡፡ እናት ወገቧ
እየተንቀጠቀጠ እግሯ እየተብረከረከ ስለተቸገረች በቆመችበት ቦታ ላይ ቁጢጥ አለች።
"ምነው አመመሽ እንዴ?" አሉ ጎረቤቷ ወይዘሮ ተዋበች። መልስ አልሰጠቻቸውም፡፡ መናገር አቃታት።
"በይ በርቺ ከንግዲህ አንቺም ወደዚያው ወደነሱ መጠቃለልሽ አይቀርም፡፡ እስከዚያው ድረስ ግን ብቸኝነቱን ጠንከር ብለሽ መቋቋም አለብሽ አውቶቡሱ እየተመዘገዘገ ጉዞውን ወደ ፊት ቀጠለ... ዳገት ቁልቁለቱን
ጋራ ሽንተረሩን ጫካና ሜዳውን እያቆራረጠ ወደ ፊት ተወነጨፈ
የባሌ ደን መቼም ለጉድ ነው፡፡ ዘይኑ የደኑን ውበት እያደነቀች አሻግራ የምታያቸው ዛፎች ሁሉ እየተነሱ የሚፈርጡ እየመሰላት
እየተገረመች ሰብስቤ ዋሻ ደረሱ፡፡ ሰብስቤ ዋሻን ቁልቁል ስትመለከተው ፍርሀት ፍርሀት አላት። እዚያ ግድም ሰማይ ተገምሶ የወደቀ ይመስላል። ከላይ ወደ ታች የሆነ ነገር ቢወረወር መሬት ለመድረስ ሳምንት የሚፈጅበት ይመስላል። መኪናው ወደ ፊት ነጎደ
"ሙጨዮ በረከቴ ኢጀ በዳ ሲንላለን! የተባረክሽ ልጅ ክፉ ዐይን አይይሽ.."እያሉ የሚመርቋት የሚወዷት ጎረቤቶቿ ትዝታ ከእናቷ ትዝታ ጋር በዐይኖቿ ላይ እየተንቀዋለለ የተራራውንና የሜዳውን ግልቢያ አሻግራ
ስትመለከት እየተደነቀች ወደ አዲስ አበባ ወደ ወንድም ጋሻዋ ከነፈች…..መኪናው በየመንገዱ ላይ እየቆመ ሸንኮራ አገዳ፣ ብርቱካን፣ ሙዝ፣ፓፓያ ለመሽጥ የሚሮጡ ልጆችን እያስተናገደ ተሳፋሪው በመስታወቱ አንገቱን ብቅ እያደረገ እየገዛ እየተቋደሰ ጉዞው ቀጠለ...
"ይህችን! ይህችን ጣፋጭ ብርቱካን! መንደሪን!. . ሙዝ አለ ሙዝ! አለ ሙዝ! ሽንኮራ ጣፋጭ ሸንኮራ አገዲ!" ሁሉም የሚሸጡትን እያወደሱ ከጣዕሙ የበለጠ በቃላት እያጣፈጡ ለመሸጥ ይሯሯጣሉ። መኪናው
በዚህ ሁኔታ ሲጓዝ ውሎ ሻሽመኔ ከተማ ደረሰ፡፡ አቶ አለሙ ዘይኑን
ይዘው ምሳ ለመብላት ወደ ኢየሩሳሌም ሆቴል ገቡ። ሆቴሉ በተስተናጋጅ እንግዶች ተጣቧል፡፡ አስተናጋጆችም ወዲያና ወዲህ ይሯሯጣሉ።
“ሄይ! ምነው ቶሎ በል እንጂ! ለአዳር አልመጣንምኮ?!"
“ምነው ባክህ ገና እያረዳችሁ ነው እንዴ? የበሰለ ወጥ ጨልፎ ለማምጣት እስከዚህ ድረስ?!.
“ከኛ በኋላ የገባው ስንቱ ተሸኘ በናታችሁ? ስማ ወንድም! መኪና ጥሎን ይሄዳልኮ ያንተን ሩጫ ለማየት አልመጣንም " ከሁሉም የሚሰነዘራውን ወቀሳ የሚስማው አስተናጋጅ.."እሺ ጌታዬ ይደርሳል አሁኑኑ አመጣለሁ" ለዘገየበት ይቅርታ ጠይቆ ይከንፋል። ደግሞ ይሮጣል.እሺ! እሺ! ማለቱ ተመጋቢውን ከንዴቱ ትንሽ መለስ ያደርገዋል። የተባረከ አስተናጋጅ በመሆኑ እንጂ እንደ ሌሎቹ ቢሆን ኖሮ ያንን ሁሉ ወቀሳና ዘለፋ
በትዕግስት አያሳልፈውም ነበር፡፡ ደንበኛን ላበሳጩበት ደመወዝ የሚከፈላቸው የሚመስላቸውን ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ ለስድብ የሚጋበዙም ሞልተዋል፡፡ይሄኛው ግን ፍፁም የተለየ ነው፡፡ ዘይኑ የአቶ አለሙን ጉልበት ተደግፋ የተመጋቢዎቹን ሁኔታ“ የአስተናጋጆቹን ሩጫ ስትመለከት
ደስ አላት። አይታው የማታውቀው ድራማ ነበር፡፡ ዘይኑና አቶ አለሙ
ተራቸው ደርሶ አስተናጋጁ ያመጣላቸውን ምግብ ከበሉና ለስላሳቸውን ጠጥተው ጥቂት እረፍት ከወሰዱ በኋላ መኪናው ለመንቀሳቀስ ጥሩምባውን አሰማ፡፡ በጊዜ የተጠናቀቀው በፍጥነት ብድግ እያለ ሲወጣ የዘገየው ደግሞ ሁለቴና ሶስቴ ይመላለስበት የነበረውን በአንድ ጉርሻ እያጠቃ በፍአጥነት ተነሳ ፡፡ ከዚያም ጉዞው ቀጥሎ ሞጆ ከተማ ደረሱ፡፡
“እንግዲህ አዲስ አበባ ልንገባ ደርስናል ወንድም ጋሼሽን ልታገኝው ትንሽ ነው የቀረሽ፡፡ ደስ ይበልሽ!” አሏት፡፡ ዘይኑ ፊቷ ፈካ ።
👍2
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ሔዋን ግን ወዲያው ሀሳብ ውስጥ ገባች። ዓይኖ ሰማይ ላይ ተተከሉ ልቧ አድማስ ተሻግሮ ሄደ። አጠገቧ ያሉትን እናቷ ረሳቻቸው። በሆዷ እያወራች ከንፈሯቿም ይንቀሳቀሱ ጀመር።
«እሙዬ» ሲሉ እናቷ አሁንም ከሃሳቧ ቀሰቀሷት::
«አቤት እማ»
«አኪሙ የነገረሽን ረሳሽው? ብዙ ማሰብና መጨነቅ እኮ ይቺን ልብሽን ታባብስብሻለች ብሎሽ ነበር። እኔም ስታስቢ ሳይሽ እሰጋለሁ። ታድያ አንዳንዴ እንኳን ቀልብሽን ሰብሰብ አድርገሽ ሀሳብሽን መርሳት ብትሞክሪ ምን አለበት የኔ ልጅ? አሏት በሀዘን አስተያየት መልከት እያሏት::
«አይዞሽ እማ! አትጨነቂ ብዙም አላስብ። አልጨነቅም!» አለቻቸው አንገቷን ወደ መሬት ደፋ አድርጋ።
«አየየ…እሙዬ! ሁኔታሽንማ እያየሁት አይደል! መጨነቄማ
ምን ይቀራል ብለሽ የኔ ልጅ?»
አሏት በትካዜ አነጋገር።
ተይ እማ፡ እንደዚህማ ከሆነ እኔም የባሰ እጨነቅብሻለሁ! ባይሆን እኔም ማሰቤን እተዋለሁ። አንቺም እትጨነቂብኝ፡፡» አለቻቸው ዓይን ዓይናቸውን እያየች።
«እባክሽ እሙዬ እባክሽ! እንደው በአጠባሁሽ ጡት ገዝቼሻለሁና ይህን ሃሳብና ትካዜ የሚባል ነገር እርግፍ አድርገሽ ተይልኝ! የኔ ልጅ እባክሽ» አሏት እናቷ አይናቸው እንባ እስኪአቀር ድረስ ጭንቅ እያላቸው።
«ተይ እማ! በጡትሽማ አትገዝችኝ ጡትሽ እኮ ለኔ የአንቺነትሽ መገለጫ ነው የእኔነቴ መሰረት ነው። ጡትሽ እኮ ስጋና ደሜ ነው ለዚያውም አስተዳደጌን እንደነገርሽኝ ለዚያን ያህል ዓመት የጠባሁት፡፡ ስለዚህ እማ! ግዝትሽን አወርጅልኝ ድንገት ተሳስቼ ሀሳብ ውስጥ የገባሁ እንደሆነ ግዝት መተላለፌ ሲሰማኝ ይበልጥኑ እጨነቅብሻለሁ እማ! አሁኑኑ ግዝትሽን አንሺልኝ እባክሽ የኔ እናት » ስትል እጆቿን እያርገበገበች ተማፀኘቻቸው።
«እሺ የኔ ልጅ፣አወርጄልሻለሁ ::" አሏት እንባቸው ከዓይናቸው ላይ እየወረደ።
«እወድሻለው እማ!» አለችና ሄዋንም እንባዋን ከዓይኗ ላይ
ትጠርግ ጀመር፡፡ ለአፍታ ያህል በመሀላቸው ፀጥታ ሰፈነ።
«ግን እሙዬ!» ሲሉ እንደገና ጠሯት።
«አቤት እማ!»
«እንደው ለዛ ልጅ ደብዳቤ ፅፈሽለት ታውቅያለሽ?» ሲሉ ጠየቋት ወደ ዛሬዋ ዋና ጉዳያቸው
ጠጋ ጠጋ ለማለት ፈልገው፡፡
«ለማን ለአስቻለው?»
«እ»
«የት ብዬ እማ! አድራሻውን ባውቅማ ኖሮ ደብዳቤ ከመጻፍ ይልቅ…» ብላ ንግግሯን ቆም ስታደርግ እናቷ ቀጠሉ።
«አዎ የኔ ልጅ! ሀሳብሽ ገብቶኛል፡፡ እንኳን አንቺ እኔ ራሴ ብርርር ብዬ
ሄጄ የሆነውን ነገር እጠይቀው ነበር፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፣ የሄደበት አገር አጉል አጉል ሆነ፣ ምን ማድረግ እችላላሁ የኔ ልጅ!?» አሏት በሀሳብ ከጎኗ መሆናቸውን ለማረጋገጥ።
«ኤርትራ ትሄጂ ነበር እማ?»
«ለምን አልሄድ እሙዬ ለምን አልለፋ ለምን አልንክራተስ እኔ
እኮ ነገሩኝ ሁሉን ገብቶኛል። ሁሉን ነገር በእነኛ ወርቆች ዓይን አደል ያየሁት» አሉ ታፈሡን በልሁንና መርእድን በማስታወስ። ቀጠሉና «ያየሁት የልጁ ወትግራፍስ ቢሆን በቀላሉ የሚረሳኝ ሆኖ ነው? ባልወልደውም ልጄ ይመስለኛል። እንደ ወለላ የረጋ መሆኑን አውቄዋለሁ!» አሏትና እንባቸውን ከዓይናቸው ላይ ጥርግ አረጉት፡፡
በዚህ ጊዜ ሔዋን ያ ሽዋዬ ለአባትና ለእናቷ የጻፈችባት ደብዳቤ አላት።በዚያ ምክንያት በእሷም ሆነ በአስቻለው ላይ አድሮ የነብረ ስጋት ታሰባትና
ዋይ ዋይ! አለች በሆዷ። ምነው ይኸን የእናቴን ሀሳብ አውቄው ቢሆን አስቹ።
ያኔ እንዲያ እየተጨነኩ ሳስጨንቅህ! እንዲያ እያለቀስኩ ሳስለቅስህ ያን ያህል ስለኔ ስትጨነቅና ስትጠበብ ኖረህ ዛሬ እናተረ ለአንተ ያላትን እምነትና ግምት አውቀኸው ቢሆን ኖሮ ምንኛ ደስ ባለህ ነበር? የቆሰለ መንፈስህ እንዴት በሻረልህ ነበር?
ግን ምን ዋጋ አለው? ያ ሁሉ ሲሆን ቆየና የዛሬው እድልህ እንዲህ ሆኖ ቀረ አስቹ?
የ'ኔ ሆድ ምን ላርግህ! የኔ ፍቅር እንዴት ልሁንልህ፡ በማለት ውስጥ
ውስጧን ስታስብና ስትብሰለሰል ቆየችና ድንገት ለቅሶ ፈንቅሏት እህህህ ….» በማለት ተንሰፈሰፈች።
«አንቺ እሙዬ» አሉና እናቷ ድንግጥ ብለው ከመቀመጬቸው በመነሳት ወደ እሷ ሮጡ።
«እማ ተይኝ!» አለች ሔዋን ፊቷን በጭኖቿ ላይ ድፍት አድርጋ እየተንሰቀሰቀች።
«እባክሽ እሙዬ እባክሽ የኔ ልጅ እባክሽ! አረ እንደው እባክሽ?» በማለት አንገቷን እቅፍ አድርገው እሳቸውም እያለቀሱ ይለምኗት ጀመር፡፡
ሔዋን ግን እሺ አላለችም። «እንቺ የማታውቂው ብዙ ነገር በሆዴ አለ እኮ እማ! » አለች አሁንም እያለቀሰች፡፡ በዚያው ቀጠለችና አስቻለው እኮ አብሮኝ የቆየው እያለቀሰ ነው እማ ትቶኝም የሄደው እያዘነ ነው እማ አስቻለው እኮ እኔን ሲል ያላየው መከራ የለም እማዬ! ያልቀመስዉ አበሳ የለም እኮ ወደ ኤርትራ እንዲሄድ ያደረኩት እኔ እራሴ ነኝ እማ! በዚያ ላይ የሄደበት አገር ጦርነት ነው።
የዋይታና የኡኡታ ምድር ነው፡፡ አስቻለው እኮ የሚታየኝ በዚህ ሀሉ የስው ልጅ አበሳና መከራ ውስጥ ሆኖ ነው።አስቻለው ሁል ጊዜ ሲደማ ይታየኛል ሁልጊዜ ሲቆስል ይሰማኛል፡፡ አንዳንዴማ ሞቶ ሬሳው በአውሬ ሲጎተት ይታየኛል፡፡
ስቃዩ መከራው ሁሉ በእዝነ-ልቦናዬ ውስጥ አልጠፋ አለ እማ! ታዲያ እንዴት ላድርግ እማ? እንዴት ልሁነው እማ እንዴትስ አይጨንቀኝ እንዴትስ አይጥበበኝ እማ!» አለችና እሁንም «እህህህ…» በማለት በለቅሶ ተንሰፈሰፈች።
«እሱን ማሪያም ትጠብቀዋለች የኔ ልጅ እመዬ እባክሽ አታልቅሽብኝ፤
እባክሽ በአጠባሁሽ ጡት! እሙዬ አሁን ዝም በይ በቃ ተይው የኔ ልጅ» በማለት እናቷ እየተርገበገቡ ለመኗት
ሔዋን ግን ለቅሶዋ ሊበርድ እንባዋ ሊቆም አልቻለም፤ አሁንም እያለቀሰች «እት አበባ እኮ፣ እት-አበባ እኮ..» ብላ ልትቀጥል ስትል ነገሩን ተወት አደረገችው፡፡ አንደበተ ቁጥቧ ሔዋን የቱንም ያህል ያስከፋቻት ቢሆን ሽዋዬን
በእናቷ ፊት መውቀስ አልፈለገችም፡፡ ብቻ እንጀቷ እስከሚሰፈሰፍ ድረስ አሁንም
በለቅሶ ተንሰቀሰቀች።
እናቷ ግን ገብቷቸዋል፡፡ «እሷን ተያት እውዬ! ያቺን አረመኔ ተያት የኔ ልጄ ያችን ጨካኝ ተያት እሙ
እኔ ገብቶኝ የለ! ተረድቼው የለ!
እባክሽ የን ልጅ ማልቀሱ አይጠቅምም።እባክሽ ዝም በይልኝ!» ሲሉ ተማፀኗት እሳቸውም እያለቀሱ።
«እ...እሺ እማ፣ ዝ..ዝም እላለሁ ቁጭ በይ!» አለቻቸው ድምጿ፤ በሲቃ እየተቆራረጠና በእንባ የራሰ ፊቷን በመጠራረግ።
የሔዋን እናት እያለቀሱ አጠገቧ ቁጭ አሉና ዓይን ዓይኗን ያዩት ጀመር። ከትንሽ ቆይታ በኋሳ ሔዋን በረድ እያላች መጣች። ለአፍታ ያህል ፀጥታ ሰፈነ ግን ደሞ ሔዋን ሀሳብ ውሰጥ ገባች ያን የሰሜን ኢትዮጽያ ክፍል በሃሳብ ትዳስሰው ጀመር ወደዚያ ለመሄድ እንዳታስብ እንኳ እንቅፋት የሆናትን ስለ አካባቢው ያላትን ግንዛቤ ሁሉ ታሰላስል ጀመር።
አዎ፤ ያ ሰሜን ኢትዮጵያ! የጥንት ስልጣኔ መነሻ፤ የውጭ ወራሪዎች መግቢያ መውጫ! በዘመናቱ አንገታቸውን ብቅ እያረጉ ሲሰልሱት የኖረና እያወደሙም ቢሆን የወደሙበት የዘመናት የጦር አውድማ! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፣የውጭ ወራሪዎች በፈጠሩት መዘዝ ወንድም ከወንድሙ እየተጋጨ አንተም ተው አንተም ተው' የሚል ጠፍቶ የእርስ በእርስ መጨራረሻ ሆኖ የቀረ የደም መሬት ያ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ሔዋን ግን ወዲያው ሀሳብ ውስጥ ገባች። ዓይኖ ሰማይ ላይ ተተከሉ ልቧ አድማስ ተሻግሮ ሄደ። አጠገቧ ያሉትን እናቷ ረሳቻቸው። በሆዷ እያወራች ከንፈሯቿም ይንቀሳቀሱ ጀመር።
«እሙዬ» ሲሉ እናቷ አሁንም ከሃሳቧ ቀሰቀሷት::
«አቤት እማ»
«አኪሙ የነገረሽን ረሳሽው? ብዙ ማሰብና መጨነቅ እኮ ይቺን ልብሽን ታባብስብሻለች ብሎሽ ነበር። እኔም ስታስቢ ሳይሽ እሰጋለሁ። ታድያ አንዳንዴ እንኳን ቀልብሽን ሰብሰብ አድርገሽ ሀሳብሽን መርሳት ብትሞክሪ ምን አለበት የኔ ልጅ? አሏት በሀዘን አስተያየት መልከት እያሏት::
«አይዞሽ እማ! አትጨነቂ ብዙም አላስብ። አልጨነቅም!» አለቻቸው አንገቷን ወደ መሬት ደፋ አድርጋ።
«አየየ…እሙዬ! ሁኔታሽንማ እያየሁት አይደል! መጨነቄማ
ምን ይቀራል ብለሽ የኔ ልጅ?»
አሏት በትካዜ አነጋገር።
ተይ እማ፡ እንደዚህማ ከሆነ እኔም የባሰ እጨነቅብሻለሁ! ባይሆን እኔም ማሰቤን እተዋለሁ። አንቺም እትጨነቂብኝ፡፡» አለቻቸው ዓይን ዓይናቸውን እያየች።
«እባክሽ እሙዬ እባክሽ! እንደው በአጠባሁሽ ጡት ገዝቼሻለሁና ይህን ሃሳብና ትካዜ የሚባል ነገር እርግፍ አድርገሽ ተይልኝ! የኔ ልጅ እባክሽ» አሏት እናቷ አይናቸው እንባ እስኪአቀር ድረስ ጭንቅ እያላቸው።
«ተይ እማ! በጡትሽማ አትገዝችኝ ጡትሽ እኮ ለኔ የአንቺነትሽ መገለጫ ነው የእኔነቴ መሰረት ነው። ጡትሽ እኮ ስጋና ደሜ ነው ለዚያውም አስተዳደጌን እንደነገርሽኝ ለዚያን ያህል ዓመት የጠባሁት፡፡ ስለዚህ እማ! ግዝትሽን አወርጅልኝ ድንገት ተሳስቼ ሀሳብ ውስጥ የገባሁ እንደሆነ ግዝት መተላለፌ ሲሰማኝ ይበልጥኑ እጨነቅብሻለሁ እማ! አሁኑኑ ግዝትሽን አንሺልኝ እባክሽ የኔ እናት » ስትል እጆቿን እያርገበገበች ተማፀኘቻቸው።
«እሺ የኔ ልጅ፣አወርጄልሻለሁ ::" አሏት እንባቸው ከዓይናቸው ላይ እየወረደ።
«እወድሻለው እማ!» አለችና ሄዋንም እንባዋን ከዓይኗ ላይ
ትጠርግ ጀመር፡፡ ለአፍታ ያህል በመሀላቸው ፀጥታ ሰፈነ።
«ግን እሙዬ!» ሲሉ እንደገና ጠሯት።
«አቤት እማ!»
«እንደው ለዛ ልጅ ደብዳቤ ፅፈሽለት ታውቅያለሽ?» ሲሉ ጠየቋት ወደ ዛሬዋ ዋና ጉዳያቸው
ጠጋ ጠጋ ለማለት ፈልገው፡፡
«ለማን ለአስቻለው?»
«እ»
«የት ብዬ እማ! አድራሻውን ባውቅማ ኖሮ ደብዳቤ ከመጻፍ ይልቅ…» ብላ ንግግሯን ቆም ስታደርግ እናቷ ቀጠሉ።
«አዎ የኔ ልጅ! ሀሳብሽ ገብቶኛል፡፡ እንኳን አንቺ እኔ ራሴ ብርርር ብዬ
ሄጄ የሆነውን ነገር እጠይቀው ነበር፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፣ የሄደበት አገር አጉል አጉል ሆነ፣ ምን ማድረግ እችላላሁ የኔ ልጅ!?» አሏት በሀሳብ ከጎኗ መሆናቸውን ለማረጋገጥ።
«ኤርትራ ትሄጂ ነበር እማ?»
«ለምን አልሄድ እሙዬ ለምን አልለፋ ለምን አልንክራተስ እኔ
እኮ ነገሩኝ ሁሉን ገብቶኛል። ሁሉን ነገር በእነኛ ወርቆች ዓይን አደል ያየሁት» አሉ ታፈሡን በልሁንና መርእድን በማስታወስ። ቀጠሉና «ያየሁት የልጁ ወትግራፍስ ቢሆን በቀላሉ የሚረሳኝ ሆኖ ነው? ባልወልደውም ልጄ ይመስለኛል። እንደ ወለላ የረጋ መሆኑን አውቄዋለሁ!» አሏትና እንባቸውን ከዓይናቸው ላይ ጥርግ አረጉት፡፡
በዚህ ጊዜ ሔዋን ያ ሽዋዬ ለአባትና ለእናቷ የጻፈችባት ደብዳቤ አላት።በዚያ ምክንያት በእሷም ሆነ በአስቻለው ላይ አድሮ የነብረ ስጋት ታሰባትና
ዋይ ዋይ! አለች በሆዷ። ምነው ይኸን የእናቴን ሀሳብ አውቄው ቢሆን አስቹ።
ያኔ እንዲያ እየተጨነኩ ሳስጨንቅህ! እንዲያ እያለቀስኩ ሳስለቅስህ ያን ያህል ስለኔ ስትጨነቅና ስትጠበብ ኖረህ ዛሬ እናተረ ለአንተ ያላትን እምነትና ግምት አውቀኸው ቢሆን ኖሮ ምንኛ ደስ ባለህ ነበር? የቆሰለ መንፈስህ እንዴት በሻረልህ ነበር?
ግን ምን ዋጋ አለው? ያ ሁሉ ሲሆን ቆየና የዛሬው እድልህ እንዲህ ሆኖ ቀረ አስቹ?
የ'ኔ ሆድ ምን ላርግህ! የኔ ፍቅር እንዴት ልሁንልህ፡ በማለት ውስጥ
ውስጧን ስታስብና ስትብሰለሰል ቆየችና ድንገት ለቅሶ ፈንቅሏት እህህህ ….» በማለት ተንሰፈሰፈች።
«አንቺ እሙዬ» አሉና እናቷ ድንግጥ ብለው ከመቀመጬቸው በመነሳት ወደ እሷ ሮጡ።
«እማ ተይኝ!» አለች ሔዋን ፊቷን በጭኖቿ ላይ ድፍት አድርጋ እየተንሰቀሰቀች።
«እባክሽ እሙዬ እባክሽ የኔ ልጅ እባክሽ! አረ እንደው እባክሽ?» በማለት አንገቷን እቅፍ አድርገው እሳቸውም እያለቀሱ ይለምኗት ጀመር፡፡
ሔዋን ግን እሺ አላለችም። «እንቺ የማታውቂው ብዙ ነገር በሆዴ አለ እኮ እማ! » አለች አሁንም እያለቀሰች፡፡ በዚያው ቀጠለችና አስቻለው እኮ አብሮኝ የቆየው እያለቀሰ ነው እማ ትቶኝም የሄደው እያዘነ ነው እማ አስቻለው እኮ እኔን ሲል ያላየው መከራ የለም እማዬ! ያልቀመስዉ አበሳ የለም እኮ ወደ ኤርትራ እንዲሄድ ያደረኩት እኔ እራሴ ነኝ እማ! በዚያ ላይ የሄደበት አገር ጦርነት ነው።
የዋይታና የኡኡታ ምድር ነው፡፡ አስቻለው እኮ የሚታየኝ በዚህ ሀሉ የስው ልጅ አበሳና መከራ ውስጥ ሆኖ ነው።አስቻለው ሁል ጊዜ ሲደማ ይታየኛል ሁልጊዜ ሲቆስል ይሰማኛል፡፡ አንዳንዴማ ሞቶ ሬሳው በአውሬ ሲጎተት ይታየኛል፡፡
ስቃዩ መከራው ሁሉ በእዝነ-ልቦናዬ ውስጥ አልጠፋ አለ እማ! ታዲያ እንዴት ላድርግ እማ? እንዴት ልሁነው እማ እንዴትስ አይጨንቀኝ እንዴትስ አይጥበበኝ እማ!» አለችና እሁንም «እህህህ…» በማለት በለቅሶ ተንሰፈሰፈች።
«እሱን ማሪያም ትጠብቀዋለች የኔ ልጅ እመዬ እባክሽ አታልቅሽብኝ፤
እባክሽ በአጠባሁሽ ጡት! እሙዬ አሁን ዝም በይ በቃ ተይው የኔ ልጅ» በማለት እናቷ እየተርገበገቡ ለመኗት
ሔዋን ግን ለቅሶዋ ሊበርድ እንባዋ ሊቆም አልቻለም፤ አሁንም እያለቀሰች «እት አበባ እኮ፣ እት-አበባ እኮ..» ብላ ልትቀጥል ስትል ነገሩን ተወት አደረገችው፡፡ አንደበተ ቁጥቧ ሔዋን የቱንም ያህል ያስከፋቻት ቢሆን ሽዋዬን
በእናቷ ፊት መውቀስ አልፈለገችም፡፡ ብቻ እንጀቷ እስከሚሰፈሰፍ ድረስ አሁንም
በለቅሶ ተንሰቀሰቀች።
እናቷ ግን ገብቷቸዋል፡፡ «እሷን ተያት እውዬ! ያቺን አረመኔ ተያት የኔ ልጄ ያችን ጨካኝ ተያት እሙ
እኔ ገብቶኝ የለ! ተረድቼው የለ!
እባክሽ የን ልጅ ማልቀሱ አይጠቅምም።እባክሽ ዝም በይልኝ!» ሲሉ ተማፀኗት እሳቸውም እያለቀሱ።
«እ...እሺ እማ፣ ዝ..ዝም እላለሁ ቁጭ በይ!» አለቻቸው ድምጿ፤ በሲቃ እየተቆራረጠና በእንባ የራሰ ፊቷን በመጠራረግ።
የሔዋን እናት እያለቀሱ አጠገቧ ቁጭ አሉና ዓይን ዓይኗን ያዩት ጀመር። ከትንሽ ቆይታ በኋሳ ሔዋን በረድ እያላች መጣች። ለአፍታ ያህል ፀጥታ ሰፈነ ግን ደሞ ሔዋን ሀሳብ ውሰጥ ገባች ያን የሰሜን ኢትዮጽያ ክፍል በሃሳብ ትዳስሰው ጀመር ወደዚያ ለመሄድ እንዳታስብ እንኳ እንቅፋት የሆናትን ስለ አካባቢው ያላትን ግንዛቤ ሁሉ ታሰላስል ጀመር።
አዎ፤ ያ ሰሜን ኢትዮጵያ! የጥንት ስልጣኔ መነሻ፤ የውጭ ወራሪዎች መግቢያ መውጫ! በዘመናቱ አንገታቸውን ብቅ እያረጉ ሲሰልሱት የኖረና እያወደሙም ቢሆን የወደሙበት የዘመናት የጦር አውድማ! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፣የውጭ ወራሪዎች በፈጠሩት መዘዝ ወንድም ከወንድሙ እየተጋጨ አንተም ተው አንተም ተው' የሚል ጠፍቶ የእርስ በእርስ መጨራረሻ ሆኖ የቀረ የደም መሬት ያ
👍7❤1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ከንስሐ ስትወጣ መቅሰፍት ተከተላት። እሷና ኢያሱ በነገሡ በአስራ ስድስተኛ ዓመታቸው ላይ አንድ ጠዋት ምንትዋብ ወደ ጸሎት ቤት ልትሄድ ስትዘጋጅ፣ አንደኛዋ ደንገጡሯ መጥታ፣ “ኧረ እቴጌ ሰማይ ምድሩ ዕርድ መስሏል” አለቻት፣ ቢጫ ስለለበሰው ሰማይና መሬት።
“እንዴት?”
“እንዲህ ዕርድ ሲመስል በነገታው አንበጣ ይወራል አሉ። ደሞም
ንፋስ እየነፈሰ ነው፣ ሰማዩም ደመና አዝሏል። ሁለቱም ነገሩን
ያባብሱታል።”
ፈጠን ብላ ወደ መስኮቱ ሄደች ምንትዋብ። እውነትም የጐንደር
ሰማይ ቢጫ ሆኗል። አፏን በእጇ ይዛ፣ “ምን ጉድ ነው? ምን ይሻላል?” አለች።
“እግዚኦ ማለት ነው እንጂ ሌላ ምን አለ?” አለች፣ ደንገጡሯ።
ኢያሱ መቸም ይሰማል... ይነግሩታል ኣለች ምንትዋብ፣ ለራሷ።
ካህናቱ በፍጥነት ጸሎት እንዲይዙ መልዕክት ላከችባቸው። ጸሎት
ቤቷ ለመሄድ ወጥታ ተመልሳ እልፍኟ ተቀመጠች። ሰማይና ምድሩ እንደዛ ሆኖ ስታየው አስፈራት።
በማግሥቱ የአንበጣ መንጋ ሰማዩን አለበሰው። የአንድ ቀን ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀናት በመቆየቱ ቤተመንግሥትም ጐንደርም ተጨነቁ፤ተጠበቡ። ሕዝቡ፣ “እግዚኦ” አለ። ታላቅ መቅሰፍት እንደመጣ አመነ።
ምሽት ላይ ሳይቀር አንበጦች ሰማዩን አንለቅ አሉ። ከባድ ዝናብና
ንፋስ ወረራውን አባባሱት።
ውሎ አድሮም ሰብል ተበላሽ። እየቆየ ሲሄድ ጐንደር ትልቅ ችግር
ላይ ስትወድቅ፣ ሕዝቧንና እንስሳዋን ረሐብ አጠወለገው፤ በሽታ አጣደፈው። ቀናትና ወራት እያለፉ ሲመጡ ቀባሪ እስኪጠፋ ሙታን በየወደቁበት ቀሩ። የተረፉት ከነገሥታቱ ጀምሮ በኃይለኛ ጉንፋን ተያዙ። እንዲህ እያለ ሁለት ዓመት አለፈ።
ሰዉ ካደረሰበት ጉዳት ገና ሳያገግም፣ ተምች በመመለሱ ችግር ብቻ ሳይሆን፣ ከቀድሞው የበለጠ ረሐብ ገባ።
ጌታችን ወርዶ ከባሕር፣
ኣዳምን ዋና ሊያስተምር፣
አፋፍ ላይ ሁነን ብናየው፣
እያጣ አለቀ ሰው።
ተብሎ እንደተገጠመው ሁሉ ጐንደርን ጨምሮ በደጋም በቆላም ሰው አለቀ። ከቤተመንግሥት የተቻለውን ያህል የእህል እርዳታ ቢደረግ እያደር ዐቅም አነሰ። የቻለ ጐንደርና አካባቢዋን ጥሎ ተሰደደ ::መሬቱን፣ ንብረቱንና ደብሩን ጥሎ መሄድ ያልሆነለት ለረሐብና ለበሽታ ተጋለጠ።
ጐንደሬዎች የሕይወት ምልክቱ ከፊታቸው ላይ ጠፍቶ ባዶው ላይ
አፈጠጡ። ከንፈራቸው ሐሩርና ውርጭ የመታው ይመስል ከስሞ፣
ቆዳቸው ተሰነጣጥቆ፣ የአንገታቸው ቆዳ ተንጠልጥሎ፣ የጉንጫቸው አጥንት አፈንግጦ፣ የሰለሉ እጆችና እግሮቻቸውን ማንሳት ተስኗቸው በረሐብ፣ በጥምና በበሽታ ተንጠራወዙ።
መከራ በሰዎች ገጽታ ላይ ግዘፍ ነሥቶ ታየ።
ለእናት፣ ለአባትና ለልጅ ቀባሪ የሚሆን ዐቅም ጠፍቶ ጐንደሬዎች
ዐይናቸው ቦዞ፣ እንባቸው ደርቆ፣ እጅና እግራቸው ዝሎ ተቀመጡ።
ትናንት ስቀው፣ ወደው፣ ጠልተው ከቶውንም በልተው የማያውቁ
መሰሉ። ዛሬ ተስፋቸውን ተነጥቀው ከሞት ጋር ተፋጠጡ። ነገ የእነሱ እንዳልሆነች አውቀው እጃቸውን ለሞት ሰጡ።
ሞት፣ ያ የሰው ልጅ የቁም ቅዠት አላስደነግጥ አለ። እንደተራ
ነገር ተቆጠረ። ጐንደሬዎች የሚዘክራቸው መላዕክትና ቅዱሳን ሁሉ ወዴት እንደሄዱ ጠየቁ። የእግዚአብሔርንም መኖሪያ አጠያየቁ። እንደ ዳዊት፣ “ጆሮን የፈጠረ አይሰማምን? ዐይንን የፈጠረ አያይምን?” ብለው
አቤቱታ አስገቡ። ሕጻናት ጡት አፋቸው እንደሸጎጡ እናቶቻቸው
እቅፍ ውስጥ ለዘላለም አሽለቡ።
ጐንደር ጉልበቷ ዛለ።
“ግዝየ ምንድነው?”
1748 ዓ.ም ለምንትዋብ ሆነ ለሃገሪቱ ጥሩ ዓመት አልሆን አለ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በጽኑ ታመመ። እናቴ ትጨነቃለች ብሎ
መታመሙን ደበቀ። ለሀያ አምስት ዓመታት ከእናቱ ጋር በስምምነት፣
በምክክርና በሰላም የገዛው ዳግማዊ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሐሙስ ሰኔ 21 ቀን ዐረፈ። የሕመሙ መንስኤ ባይታወቅም፣ የግራዝማች ኢያሱ እኅት የወንድሟን ደም ለመበቀል መርዝ አብልታው ነው የሚል ወሬ
ጐንደር ውስጥ ተዛመተ፡፡
አሳዛኙ ዜና ለምንትዋብ ደረሳት። ስትበር ልጂጋ ሄደች።
የምትሳሳለት ልጇ በሞት ተለይቷታል። ጉልበቷ ከዳት፤ መቀነቷን ፈታች። ጮኸች። አበደች። “ወዮልኝ ልጄ! ወዮልኝ ውዱ ልቼ! የዐይኖቼ ብርሃን! የልቤ ደስታ! ወዮልኝ ልጄ” እያለች ደረቷን ደቃች፣እየወደቀች ተነሳች፣ ፀጉሯን ነጨች፤ ፊቷን ቧጠጠች።
“የላስታን ዓቀባት ያለፈረስ ያለበቅሎ የወጣህ፣ እንዴት ታሰረ
እግርህ። አገር አንድ ለማረግ እንዳልጣርኸው፣ ጫካ ገብተህ አድነህ እንዳልመጣህ፣ ኸነብር ኻንበሳ ጋር ተጋፍጠህ እንዳላሸነፍህ፣ አሁን ማን እግርህን በገመድ አሰረህ?” እያለች አነባች።
ራሷን እስከመሳት ደረሰች።
“ያ እንደ አንበሳ ሚያስገመግመው ድምፅህ የት ጠፋ? ምን ነበር
እመምህ? መታመመህን ያልነገርኸኝ ምን ሁነህ ነው? ያላንተ ማን አለኝ? የአባትህ ዐደራ ነህ። አንተ ለኔ አባቴ፣ እናቴ፣ እህቴ፣ ወንድሜ፣ ጋሻ መከታዬ፣ ክብሬ፣ ሁሉ ነገሬ ነህ። አሁን ምን ይበጀኛል ልዤ? ኸንግድህ እንዴት ልኖር ነው? እንድህ አልጋ ላይ ተኝተህ ኸማይህ ሞቶ መቀበር ይሻለኝ ነበረ” እያለች ጮኸች።
ወዳጅ፣ ዘመድ፣ መኳንንትና ሌሎችም ለመያዝ አቃታቸው።
“ጠንካራው ማንነትሽ የት ኸደ? እርጋታሽ... አስተዋይነትሽ የት ኸደ? አሁንም ይች አገር ባንቺ ዠርባ ላይ ናት። እንምከር... ሁሉንም ነገር በቅጡ እናርገው” ሲሉ ተማጸኗት።
እሷ ግን መጽናናት አልሆነላትም።
“ማነው እንዳንተ ኸንጉሥ የተገኘ ዠግና ወንድ ልዥ፣ ለጠላቶቹ
ማይመለስ፣ ክንዱ ማይዝል? እንዳንተ ይቅር ባይ፣ ማነው እንዳንተ በሃይማኖቱ ጽኑ? ለድኻ ሚራራ፣ ሚዘክር፣ ማነው? እንዳተ የድኻውን ሮሮ ሰሚ፣ ማነው እንዳንተ ፍርድ ጎደለ፣ ደኻ ተበደለ ብሎ ውነት ፈራጅ? ማነው እንዳንተ አገር ወዳጅ? እንዳተ የናቱን ምክር ሰሚ፣ ማነው? እንዳንተ ታላቆቹን ኣክባሪ፣ ማነው? እንዳንተ ሸጋ ማነው?
እንዳንተ ጥርሰ መልካም፣ እንዳንተ ዕንቁ፣ እንዳንተ ወርቅ ማነው?
አሁን ምን ላርግ? የት ልኸድ? የት ልግባ? ቀድሞ በሕይወትህ
አስደስትኸኝ፣ አሁን በሞትህ አነደድኸኝ” እያለች ዋይታዋ ማባሪያ ኣጣ።
በአጎቷ በደጅአዝማች እሸቴ ራስቢትወደድ ወልደልዑልን
አስጠራች። ወልደልዑል ሲሰማ ሲሮጥ መጣ፤ አበደ፤ ጨርቁን ጣለ።እንደ እሱ የኢያሱን መሞት ያልሰሙ መኳንንት መጉረፍ ሲጀምሩ፣ እንደገና ዋይታና ሰቆቃ ሆነ። ጩኸትና ዋይታ ከዳር እዳር አስተጋባ።
ጩኸቱና ዋይታው ወህኒ አምባ ከመድረሱ ቀደም ብሎ እልፍኝ
አስከልካዮች የብርሃን ሰገድ ኢያሱ አስከሬን ያለበትን ቤተመንግሥት ቆለፉ። ወልደልዑል በአስቸኳይ መደረግ ወዳለበት ነገር ትኩረቱን
አደረገ ምንትዋብን፣ “እቴ ብርሃን ሞገሳ ሆይ፣ ብርሃን ሰገድ
ልዥሽ በሕይወት ሳለ ምን ነግሮሽ ነበር? መንበረ መንግሥቱን ማን
እንደሚወርስ አልነገረሽም? ኸሦስቱ ልዦቹ ከአቤቶ አፅቁ፣ ከአቤቶ ኃይሉና ከአቤቶ ዋዩ መኻል የትኛው ይንገሥ አለ? የነገረሽ ኻለ እባክሽ ንገሪን” ሲል ወተወታት።
“ኸመቤት ውቢት የተወለደው አቤቶ ዋዩ በእኔ መንበረ መንግሥት ይቀመጥ። ዮዳኤ የሰባት ዓመቱን ኢዮአስን እንዳነገሠው እናንተም
ልጄን ኢዮአስን አንግሡት፤ እኔንም አባቴን በካፋንም ሊተካ ይችላል።
ምወደው እሱን ነው” ብሏል፣ አለቻቸው ሲቃ እየተናነቃት።
ወልደልዑል፣ የቅርብ ዘመዶችና የቅርብ መኳንንት በር ዘግተውና
በነፍጥ አስጠብቀው መከሩ። አቤቶ ዋዩ ወይንም ኢዮአስ ገና የሰባት ዓመት ልጅ ነበርና፣ “እቴጌ በነበረችበት ሥልጣን ትቀጥል” ብለው ወሰኑ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ከንስሐ ስትወጣ መቅሰፍት ተከተላት። እሷና ኢያሱ በነገሡ በአስራ ስድስተኛ ዓመታቸው ላይ አንድ ጠዋት ምንትዋብ ወደ ጸሎት ቤት ልትሄድ ስትዘጋጅ፣ አንደኛዋ ደንገጡሯ መጥታ፣ “ኧረ እቴጌ ሰማይ ምድሩ ዕርድ መስሏል” አለቻት፣ ቢጫ ስለለበሰው ሰማይና መሬት።
“እንዴት?”
“እንዲህ ዕርድ ሲመስል በነገታው አንበጣ ይወራል አሉ። ደሞም
ንፋስ እየነፈሰ ነው፣ ሰማዩም ደመና አዝሏል። ሁለቱም ነገሩን
ያባብሱታል።”
ፈጠን ብላ ወደ መስኮቱ ሄደች ምንትዋብ። እውነትም የጐንደር
ሰማይ ቢጫ ሆኗል። አፏን በእጇ ይዛ፣ “ምን ጉድ ነው? ምን ይሻላል?” አለች።
“እግዚኦ ማለት ነው እንጂ ሌላ ምን አለ?” አለች፣ ደንገጡሯ።
ኢያሱ መቸም ይሰማል... ይነግሩታል ኣለች ምንትዋብ፣ ለራሷ።
ካህናቱ በፍጥነት ጸሎት እንዲይዙ መልዕክት ላከችባቸው። ጸሎት
ቤቷ ለመሄድ ወጥታ ተመልሳ እልፍኟ ተቀመጠች። ሰማይና ምድሩ እንደዛ ሆኖ ስታየው አስፈራት።
በማግሥቱ የአንበጣ መንጋ ሰማዩን አለበሰው። የአንድ ቀን ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀናት በመቆየቱ ቤተመንግሥትም ጐንደርም ተጨነቁ፤ተጠበቡ። ሕዝቡ፣ “እግዚኦ” አለ። ታላቅ መቅሰፍት እንደመጣ አመነ።
ምሽት ላይ ሳይቀር አንበጦች ሰማዩን አንለቅ አሉ። ከባድ ዝናብና
ንፋስ ወረራውን አባባሱት።
ውሎ አድሮም ሰብል ተበላሽ። እየቆየ ሲሄድ ጐንደር ትልቅ ችግር
ላይ ስትወድቅ፣ ሕዝቧንና እንስሳዋን ረሐብ አጠወለገው፤ በሽታ አጣደፈው። ቀናትና ወራት እያለፉ ሲመጡ ቀባሪ እስኪጠፋ ሙታን በየወደቁበት ቀሩ። የተረፉት ከነገሥታቱ ጀምሮ በኃይለኛ ጉንፋን ተያዙ። እንዲህ እያለ ሁለት ዓመት አለፈ።
ሰዉ ካደረሰበት ጉዳት ገና ሳያገግም፣ ተምች በመመለሱ ችግር ብቻ ሳይሆን፣ ከቀድሞው የበለጠ ረሐብ ገባ።
ጌታችን ወርዶ ከባሕር፣
ኣዳምን ዋና ሊያስተምር፣
አፋፍ ላይ ሁነን ብናየው፣
እያጣ አለቀ ሰው።
ተብሎ እንደተገጠመው ሁሉ ጐንደርን ጨምሮ በደጋም በቆላም ሰው አለቀ። ከቤተመንግሥት የተቻለውን ያህል የእህል እርዳታ ቢደረግ እያደር ዐቅም አነሰ። የቻለ ጐንደርና አካባቢዋን ጥሎ ተሰደደ ::መሬቱን፣ ንብረቱንና ደብሩን ጥሎ መሄድ ያልሆነለት ለረሐብና ለበሽታ ተጋለጠ።
ጐንደሬዎች የሕይወት ምልክቱ ከፊታቸው ላይ ጠፍቶ ባዶው ላይ
አፈጠጡ። ከንፈራቸው ሐሩርና ውርጭ የመታው ይመስል ከስሞ፣
ቆዳቸው ተሰነጣጥቆ፣ የአንገታቸው ቆዳ ተንጠልጥሎ፣ የጉንጫቸው አጥንት አፈንግጦ፣ የሰለሉ እጆችና እግሮቻቸውን ማንሳት ተስኗቸው በረሐብ፣ በጥምና በበሽታ ተንጠራወዙ።
መከራ በሰዎች ገጽታ ላይ ግዘፍ ነሥቶ ታየ።
ለእናት፣ ለአባትና ለልጅ ቀባሪ የሚሆን ዐቅም ጠፍቶ ጐንደሬዎች
ዐይናቸው ቦዞ፣ እንባቸው ደርቆ፣ እጅና እግራቸው ዝሎ ተቀመጡ።
ትናንት ስቀው፣ ወደው፣ ጠልተው ከቶውንም በልተው የማያውቁ
መሰሉ። ዛሬ ተስፋቸውን ተነጥቀው ከሞት ጋር ተፋጠጡ። ነገ የእነሱ እንዳልሆነች አውቀው እጃቸውን ለሞት ሰጡ።
ሞት፣ ያ የሰው ልጅ የቁም ቅዠት አላስደነግጥ አለ። እንደተራ
ነገር ተቆጠረ። ጐንደሬዎች የሚዘክራቸው መላዕክትና ቅዱሳን ሁሉ ወዴት እንደሄዱ ጠየቁ። የእግዚአብሔርንም መኖሪያ አጠያየቁ። እንደ ዳዊት፣ “ጆሮን የፈጠረ አይሰማምን? ዐይንን የፈጠረ አያይምን?” ብለው
አቤቱታ አስገቡ። ሕጻናት ጡት አፋቸው እንደሸጎጡ እናቶቻቸው
እቅፍ ውስጥ ለዘላለም አሽለቡ።
ጐንደር ጉልበቷ ዛለ።
“ግዝየ ምንድነው?”
1748 ዓ.ም ለምንትዋብ ሆነ ለሃገሪቱ ጥሩ ዓመት አልሆን አለ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በጽኑ ታመመ። እናቴ ትጨነቃለች ብሎ
መታመሙን ደበቀ። ለሀያ አምስት ዓመታት ከእናቱ ጋር በስምምነት፣
በምክክርና በሰላም የገዛው ዳግማዊ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሐሙስ ሰኔ 21 ቀን ዐረፈ። የሕመሙ መንስኤ ባይታወቅም፣ የግራዝማች ኢያሱ እኅት የወንድሟን ደም ለመበቀል መርዝ አብልታው ነው የሚል ወሬ
ጐንደር ውስጥ ተዛመተ፡፡
አሳዛኙ ዜና ለምንትዋብ ደረሳት። ስትበር ልጂጋ ሄደች።
የምትሳሳለት ልጇ በሞት ተለይቷታል። ጉልበቷ ከዳት፤ መቀነቷን ፈታች። ጮኸች። አበደች። “ወዮልኝ ልጄ! ወዮልኝ ውዱ ልቼ! የዐይኖቼ ብርሃን! የልቤ ደስታ! ወዮልኝ ልጄ” እያለች ደረቷን ደቃች፣እየወደቀች ተነሳች፣ ፀጉሯን ነጨች፤ ፊቷን ቧጠጠች።
“የላስታን ዓቀባት ያለፈረስ ያለበቅሎ የወጣህ፣ እንዴት ታሰረ
እግርህ። አገር አንድ ለማረግ እንዳልጣርኸው፣ ጫካ ገብተህ አድነህ እንዳልመጣህ፣ ኸነብር ኻንበሳ ጋር ተጋፍጠህ እንዳላሸነፍህ፣ አሁን ማን እግርህን በገመድ አሰረህ?” እያለች አነባች።
ራሷን እስከመሳት ደረሰች።
“ያ እንደ አንበሳ ሚያስገመግመው ድምፅህ የት ጠፋ? ምን ነበር
እመምህ? መታመመህን ያልነገርኸኝ ምን ሁነህ ነው? ያላንተ ማን አለኝ? የአባትህ ዐደራ ነህ። አንተ ለኔ አባቴ፣ እናቴ፣ እህቴ፣ ወንድሜ፣ ጋሻ መከታዬ፣ ክብሬ፣ ሁሉ ነገሬ ነህ። አሁን ምን ይበጀኛል ልዤ? ኸንግድህ እንዴት ልኖር ነው? እንድህ አልጋ ላይ ተኝተህ ኸማይህ ሞቶ መቀበር ይሻለኝ ነበረ” እያለች ጮኸች።
ወዳጅ፣ ዘመድ፣ መኳንንትና ሌሎችም ለመያዝ አቃታቸው።
“ጠንካራው ማንነትሽ የት ኸደ? እርጋታሽ... አስተዋይነትሽ የት ኸደ? አሁንም ይች አገር ባንቺ ዠርባ ላይ ናት። እንምከር... ሁሉንም ነገር በቅጡ እናርገው” ሲሉ ተማጸኗት።
እሷ ግን መጽናናት አልሆነላትም።
“ማነው እንዳንተ ኸንጉሥ የተገኘ ዠግና ወንድ ልዥ፣ ለጠላቶቹ
ማይመለስ፣ ክንዱ ማይዝል? እንዳንተ ይቅር ባይ፣ ማነው እንዳንተ በሃይማኖቱ ጽኑ? ለድኻ ሚራራ፣ ሚዘክር፣ ማነው? እንዳተ የድኻውን ሮሮ ሰሚ፣ ማነው እንዳንተ ፍርድ ጎደለ፣ ደኻ ተበደለ ብሎ ውነት ፈራጅ? ማነው እንዳንተ አገር ወዳጅ? እንዳተ የናቱን ምክር ሰሚ፣ ማነው? እንዳንተ ታላቆቹን ኣክባሪ፣ ማነው? እንዳንተ ሸጋ ማነው?
እንዳንተ ጥርሰ መልካም፣ እንዳንተ ዕንቁ፣ እንዳንተ ወርቅ ማነው?
አሁን ምን ላርግ? የት ልኸድ? የት ልግባ? ቀድሞ በሕይወትህ
አስደስትኸኝ፣ አሁን በሞትህ አነደድኸኝ” እያለች ዋይታዋ ማባሪያ ኣጣ።
በአጎቷ በደጅአዝማች እሸቴ ራስቢትወደድ ወልደልዑልን
አስጠራች። ወልደልዑል ሲሰማ ሲሮጥ መጣ፤ አበደ፤ ጨርቁን ጣለ።እንደ እሱ የኢያሱን መሞት ያልሰሙ መኳንንት መጉረፍ ሲጀምሩ፣ እንደገና ዋይታና ሰቆቃ ሆነ። ጩኸትና ዋይታ ከዳር እዳር አስተጋባ።
ጩኸቱና ዋይታው ወህኒ አምባ ከመድረሱ ቀደም ብሎ እልፍኝ
አስከልካዮች የብርሃን ሰገድ ኢያሱ አስከሬን ያለበትን ቤተመንግሥት ቆለፉ። ወልደልዑል በአስቸኳይ መደረግ ወዳለበት ነገር ትኩረቱን
አደረገ ምንትዋብን፣ “እቴ ብርሃን ሞገሳ ሆይ፣ ብርሃን ሰገድ
ልዥሽ በሕይወት ሳለ ምን ነግሮሽ ነበር? መንበረ መንግሥቱን ማን
እንደሚወርስ አልነገረሽም? ኸሦስቱ ልዦቹ ከአቤቶ አፅቁ፣ ከአቤቶ ኃይሉና ከአቤቶ ዋዩ መኻል የትኛው ይንገሥ አለ? የነገረሽ ኻለ እባክሽ ንገሪን” ሲል ወተወታት።
“ኸመቤት ውቢት የተወለደው አቤቶ ዋዩ በእኔ መንበረ መንግሥት ይቀመጥ። ዮዳኤ የሰባት ዓመቱን ኢዮአስን እንዳነገሠው እናንተም
ልጄን ኢዮአስን አንግሡት፤ እኔንም አባቴን በካፋንም ሊተካ ይችላል።
ምወደው እሱን ነው” ብሏል፣ አለቻቸው ሲቃ እየተናነቃት።
ወልደልዑል፣ የቅርብ ዘመዶችና የቅርብ መኳንንት በር ዘግተውና
በነፍጥ አስጠብቀው መከሩ። አቤቶ ዋዩ ወይንም ኢዮአስ ገና የሰባት ዓመት ልጅ ነበርና፣ “እቴጌ በነበረችበት ሥልጣን ትቀጥል” ብለው ወሰኑ።
👍14👏1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ
ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡
እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::
«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።
ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::
ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::
የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!
«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»
ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::
አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።
«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።
«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::
«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::
አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡
አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::
ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡
የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ገባህህ፧ «ቴናድዬ» ሲል ዦንድሬ በድጋሚ ተናገረ: ሽጉጡ ከማሪየስ እጅ ሊወድቅ ምንም ያህል አልቀረው ዦንዴሬ ማን እንደሆነ ሲናገር ከአባባ ሸበቶ ይበልጥ ማሪየስን ነው የረበሸው:: ማሪየስ ገና ስሙን ሲሰማ
ይህ ሰው ማን እንደሆነ አወቀ፡፡ አባባ ሸበቶ ግን ቶሎ አላስታወሰውም::
የዚህ ሰው ስምና ሆቴል አባቱ ትቶለት ከሞተመ ወረቀት ላይ ተጽፎአል፡፡ የአባቱን አደራ ለመጠበቅ ሲያየውና ሊጠይቀው ብዙ ጊዜ ፈልጎ አልተሳካለትም:: በመጨረሻ ግን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ተገናኘው፡፡ ለካስ
የአባቱን ሕይወት ያዳነው ሰውዬ ሽፍታ ነው! ምን የሚገርም ጉድ ነው ምን ዓይነት የሕይወት አጋጣሚ ነው? ሕይሀት ራስዋ ትቀልዳለች ሲል አሰበደ
ይህን ቴናድዬ የተባለውን ሰው ቢያገኘው እግሩ ላይ ወድቆና ጫማውን ስሞ ሊያመሰግነው ለራሱ ቃል ገብቶ ነበር፡፡ እርግጥ ነው አሁን አግኝቶታል፡፡
ነገር ግን ማመስገኑ ቀርቶ ለፍርድ አሳልፎ ሊሰጠው ነው:: ቀልድ
አይመስልም፤ ግን አይደለም::
ማሪየስ ሁኔታውን ሲያሰላስል አሳቡን መቋጨት አቃተው:: ድንገት በገጠመው ሁኔታ እንኳን አባባ ሸበቶን ሊረዳ ራሱን መቆጣጠር ተሳነው:: ነገሩ ራሱን አዞረው:: ሁኔታው እየተፋፋመ መጣ፡፡ እርሱ ግን ራሱን
ሊስት ሆነ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአሁን በኋላ ቴናድዩ እንጂ ዦንድሬ ብለን
የማንጠራው ሰው ከወዲህ ወዲያ ይንቆራጠጥ ጀመር፡፡ የኩራትና ድል የመምታት ስሜት አድሮበታል፡፡ በድንገት ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ
«ተዘፈነ! ተበላ! ተጠጣ! ተተፋ!» ሲል ጮኸ፡፡
እንደገና መንቆራጠጥ ጀመረ::
«አይገርምም» ሲል ጩኸቱን ቀጠለ፡፡ ‹‹በመጨረሻ አገኘሁህ:: የእኛ ምፅዋተኛ፤ የእኛ አዛኝ ቅቤ አንጓች የእኛ ቱጃር! የእኛ አሻንጉሊት ለጋሽ አታውቀኝም? የለም ፧ ሞንት ፈርሜ ላይ ከሆቴል ቤቴ ውስጥ ገብተህ
ያደርህ አንተ አይደለህም፧ ከስምንት ዓመት በፊት የገና እለት፤ በ1823 ዓ.ም! የፋንቲንን ልጅ ከቤቴ የወሰድከው አንተ አይደለህም! የእኛ ቀጣፊ
ያን ጊዜ ለብሰኸው የነበረው ረጅም ብጫ ካፖርት ምን ደረሰ? አለቀ? እንደዛሬ ጠዋት ጠቅልለህ ይዘኸው የነበረውስ ጨርቅ! አሁን ውጣ ከዚህ፣ ዓይንህን ያውጣውና፡፡ አንተ ሰይጣን፤ የእኛ መጽዋች! አታውቀኝም፤ እ
ይሁና፤ እኔ ግን አውቅሃለሁ:: ከዚህች ቤት ውስጥ ገና ስትገባ ነው | የለየሁህ፤ ሞላጫ! ያን ጊዜ አታለልከኝ አሞኘኸኝ:: ለእድሌ መስበር ምክንያት የሆንከው አንተ ነህ:: አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ ወርውረህልኝ ደህና ትረዳኝ፧ ታገለግለኝ የነበረችዋን ልጅ ወሰድክብኝ:: ልጅትዋ ይህን ጊዜ ብዙ ሀብት አስገኝታልኝ ነበር:: የሀብታም ወገን ስለነበረች በስምዋ ብዙ ሀብት ይመጣልኝ ነበር:: አንተ ግን ያንን ምንጭ አደረቅኸው:: ያቺን ሸቃባ ይዘክብኝ ስትጠፋ ድል ያደረገህ መስሎህ ነበር፡፡ ዛሬ ግን አታመልጠኝም፤አታሸንፈኝም:: አንተ ሽባ፤ በቀል ነው የሚታየኝ አሁን! ጻድቁ፣ ዛሬ አልቆልሃል፡፡ ደግሞ ገንዘብ ይዞልኝ መጣ እኮ! ቂል:: ዛሬ ጠዋት ሳይህ ፍዳህን እንደማስቆጥርክ ነው ለራሴ ቃል የገባሁት።
ቴናድዬ ንግግሩን አቋረጠ፡፡ ትንፋሽ አጠረው:: የሚያጨሰው ሲጃራ ፈላበት ፊቱ ግን እንደ ጠዋት ፀሐይ ፈካ፡፡ ሊዋጋ እንደሚዘል ፍየል ፈነጠዘ፡፡ አባባ ሸበቶን ከቀጥጥሩ ስር በማዋለ በጣም ደስ አለው:: ደስታው
የድንኮች ቀውሌን ጠልፎ የመጣል ፤ የቀበሮ የታመመ በሬን ዘንጥለ የመብላት ያህል ነበር፡፡ የታመመ በሬ እንዳይዋጋ አቅም ያንሰዋል፤ ዝም እንዳይል ነፍሰ አልወጣችምና ይንፈራገጣል::
ቴናድዬ ሲለፈልፍ አባባ ሸበቶ ሊያቋርጠው አልፈለገም:: ንግግሩን እስኪጨርስ ጠበቀው:: አሁን ግን ቆም ሲል እርሱ ተናገረ::
የምትለው ነገር አልገባኝም፤ ተሳስተሃል፡፡ እኔ ድሃ እንጂ ባለብዙ ብር ወይም ቱጃር አይደለሁም፡፡ አንተ ትላለህ እንጂ እኔ አንተን አላውቅህም::
ከሌላ ሰው ጋር ተምታትቼብህ ነው::
«እህ» ሲል ቴናድዬ ጮኸ፤ አሾፈ:: «አሁንም ታሾፋለህ፤ ትቀልዳለህ!
ጌታው ወጥመድ ውስጥ ነው የገባኸው:: አታስታውስማ፣ ማን እንደሆንኩ አልለየኸኝማ!
«ይቅርታህን» አለ አባባ ሸበቶ ተኮሳትሮ፧ «ሽፍታ መሆንህን እየለየሁ ነው»
ቴናድዬ የሰውዬው ድፍረት ከማስደንገጥ አልፎ በጣም አናደደው::ይዞት የነበረውን የወንበር ድጋፍ ንዴቱን የተወጣሰት ይመስል ጨምድዶ ያዘው:: ባለቤቱ «ሽፍታ» የሚለውን ቃል ስትሰማ ከአልጋ ጫፍ ተወረወረች፡፡ቴናድዬ «አትነቃነቂ» ሲል ባለቤቱን አስጠነቀቀ፡፡ ወደ አባባ ሸበቶ ዞር ብሎ ሽፍታ አልክ፤ እናንተ ሀብታሞች እኮ እኛን በዚህ ስም እንደምትጠሩን መቼ አጣነው›› ሲል በመጮህ ተናገረ::
«አዎን ተሸነፍኩልህ ፤ ይኸው ተደብቄና ተሰውሬ የሃፍረት ማቄን
ለብሼ እኖራለሁ፡፡ የምበላውና የምልሰው የለኝም:: ግን ሽፍታ ነኝ:: ይኸው ሶስት ቀኔ ነው እህል ከቀመስኩ:: አንተ ደራርበህ ለብሰሃልና ሞቆሃል::እኔን እዚህ ቆፈን ይዞ ያንቀጠቅጠኛል:: አሽከር ቀጥረህ ፎቅ ቤት ውስጥ
ትኖራለህ:: እኔ እንደ ከብት በረት አድራለሁ:: አንተ ሰሐምሌና በነሐሴ ምግብ ስታማርጥ እኛ የማሽላ ቂጣ አሮብናል:: ይህም አነሰና ሽፍታ ትለናለህ! የግሌ የሆነ ሥራ የነበረኝ ሰው ነኝ:: ከዚህም ደግሞ ይበልጥ ሁለታችንም ፈረንሳዮች በመሆናችን አስተዳዳሪ ለመምረጥ እኩል
እንሰለፋለን፡፡ በል አሁን ከላይህ ላይ ወጥተን ከመጨፈራችን በፊት
የምትናገረው ነገር ካለ ተናገር» ሲል አፈጠጠበት::
አባባ ሸበቶ ዝም አለ፡፡ በዝምታው
መካከል የፈረስ ድምፅ ስለተሰማ
ሁሉም ቀና አሉ።
«የሚፈለጥ እንጨት ካለ እኔ እፈረካክሰዋለሁ:::» መጥረቢያ በእጁ የያዘው ሰው ነበር።
«ለምንድነው ፊትህን የሸፈንክበትን ጨርቅ ያነሳኸው?» ሲል ቴናድዬ በቁጣ ጠየቀው
የያዘው ሰው ነበር-
በቁጣ ጠየቀው::
«ለመሳቅ» ሲል መለሰለት::
አባባ ሸበቶ ቁጣው ገንፍሉበት ይንቆራጠጥ የነበረውን ቴናድ።
በዓይኑ ይጠብቃል፡፡ በሩ ላይ ሦስት ዘበኞች ቆመጥ ስለሚጠብቁት ቴናድዬ በጣም ተዝናንቷል፡፡ ከዚህም በላይ ሴትዬዋ እንኳን ባትቆጠር
ዘጠኝ ለአንድ ናቸው:: ስለዚህ አባባ ሸበቶን ናቅ በማድረግ ቴናድዬ ፊቱ ወደ ባለ መጥረቢያው አዞረ፡፡
አባባ ሽበቶ በዚህች እድል ለመጠቀም ወንበሩን በእግሩ፣ ጠረጴዛው በእጁ አሽቀነጠረና በሚያስደንቅ ፍጥነት ተወርውር ለቴናድዬ ጊዜ ሳይሰጠው
ከመስኮቱ ደረሰ፡፡ መስኮቱን ለመክፈትና ለመፈናጠጥ ጊዜ አልወሰደበትም ሆኖም ገና ግማሽ ሰውነቱን እንዳስወጣ ስድስት ሰዎች ከኋላ ጉትተው ወደ
ክፍሉ መለሱት፡፡ ሦስቱ የከሰል ሠራተኞች ከላዩ ላይ ተረባረቡ፡፡ የቴናድዩ ባለቤት በወንበር ጭንቅላቱን አለችው::
ጫጫታ ሲሰሙ ጊዜ ሌሉች ውጭ ቆመው የነበሩት ሽፍቶች ወደ ውስጥ ገቡ፡፡ አልጋ ላይ ተጋድሞ የነበረው ሽማግሌ እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገደ መዶሻ ይዞ መጣ፡፡
የሞትና የሽረት ትግል ቀጠለ:: አባባ ሸበቶ አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ
በቡጢ ቢለው ሽማግሌው ከመሬት ላይ ተዘረረ: ሌሉች ሁለቱን ደግሞ አንዱን በእርግጫ ሌላውን በጡጫ ሲላቸው ጊዜ እነርሱም ከመሬት ተደፉ፡፡ ከዚያም ላያቸው ላይ ሲወጣ ጊዜ ልክ ድንጋይ እንደተጫነበት ሰው
👍16❤1
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ሳቤላ በባሏና በባርባራ ሔር ግንኙነት የነበራት ቅናት ፍራንሲዝ ሌቪሰን
ኢስት ሊን ከገባ ወዲህ ከምን ጊዜም የበለጠ ጨምሮ ታደሰባት ባርባራ በበኩሏ ሪቻርድ ባረጋገጠው መሠረት ወንጀሉን የፈጸመው ፍሬድሪክ ቶርን መሆኑን በማመን፡ የተሰወረው ምስጢር ገሃድ ሆኖ ወንድሟ ከወደቀበት ከባድ መከራ በፍርድ ነጻ ተለቆ ለማየት ከመጓጓቷ የተነሣ ልቧን ከመሳት አፋፍ ደርሳ ነበር ።በነገሩ ብታምንበትም ምንም ለማድረግ ኃይል አልነበራትም ከእንቅልፍ ይልቅ ቅዠት የበዛበት ሌሊት ዐልፎ በነጋ ቁጥር ' ' ምነው ዛሬ አንዳች የማረጋገጫ ነጥብ ባገኘሁ! ተጠርታም
ከሔርበርት ቤት ብዙ ጊዜ ተመላልሳለች የሚስተር ሔርበርት ሴት ልጆችም ባልንጀሮቿ ስለ ነበሩ ፡ ለዕረፍት ለመጣው ወንድማቸው ልዩ ዝግጅት አድር?ው ሲጠሯት ካፒቴን ቶርንን ብዙ ጊዜ አይታዋለች
እንዶዚህ በመስሉ አጋጣሚዎች ስለ ዐለፈው ታሪኩ አንዳንድ ነር ትለቃቅምና ያገኘችውን ይዛ ወደ ሚስተር ካርላይል ትሮጣለች ከቢሮው ስትሔድ ቶርን ያያት
እንደሆነ እንዳይነቃ በመፍራት ወዶ ኢስት ሊን ሔዳ አለበለዚያ ደሞ ወደ ቢሮ ሲሔድ ወይም ከቢሮ ሲመለስ ከመንገድ ጠብቃ ነበር የምታገኘው "ነገር ግን ! ይኸን ያህል የሚጠቅም ነገር ይዛ መጥታ አታውቅም » አንድ ቀን ማታ ቶርን ዱሮ
ዌስት ሊን እንደ ነበረ ልትነግረው መጣች " በሌላ ቀን ደግሞ ለይምሰል እመቤት ሳቤላን ለመጠየቅ መጣችና ሚስተር ካርይልን ለብቻው ልታነጋግረው እንደምትፈልግ ነገረችው " ተመራርተው ወጡና ኢያወሩ እስከ መናፈሻው በር አብሯት ሲሔድ ሁሉ የሳቤላ ቀናተኛ ዐይኖች ያዩዋቸዋል " ስለ ቶርን ትነግረው " የነበሩት ነጥቦች ሁሉ ጠንካራ አይደሉም እነሱንም ሚስተር ካርላይልም ቀደም ብሎ
ያውቃቸዋል " እሱ ግን መስማቱን ሳይገልጽላት በጉጉትና በስሜት ያዳምጣታል "
ሳቤላ ባሏና ባርባራ ሲገናኙ በዐይኗ አይታ ተናደደች ቁጠዋ ተቀስቅሶ የአእምሮዋ ሰላም ደፍርሶ ትትከነከናለች " ፍራንሊዝ ሌቪሰን ደግሞ እሷ ያላየቻችውን ግንኙነቶች እየተከታተለ ይነግራት ጀመር " ሚስተር ካርላይል ለጤና ይበጃል እያለ ይበልጡን ጊዜ ከቢሮ ወደ ቤት በእግሩ ይመላለስ ነበር " በሚስተር ሔር ቤት ሲያልፍ ባርባራ እየጠበቀችም ሆነ ባጋጣሚ ስታገኘው የቶርንን ነገር በምታነጋግረው ጊዜ ካፒቴን ሌቪሰን ቁጥቋጦ ለቁጥቋጦ እንደ እባብ እየተምለገለገ ሔዶ
ይመላከታቸውና እየጨማመረና እያጋነነ ለሳቤላ ይነግራት ጀመር "
ባርባራ ግን ስለ ሳቤላ ቅናት ምንም ነገር አታውቅም እሱም ሚስቱን እንደሚወድና ለሷም አንዲት የፍቅር ፊት አሳይቷት ስለማያውቅ ሳቤላ በሷ መቅናቷን ሰው ቢነግራት እንኳን በነጋሪዋ ከመሣቅ በቀር አታምንም ነበር
ዱሮ በፍቅር ትነድለት የነበረው ሁሉ ከሁኔታው ተረድታ ትታው' አሁን ካርላይል ዘንድ የሚያመላልሳት
የወንድሟ ጉዳይ ብቻ ሆኖ ነበር "
ኣንድ ቀን ጠዋት ሚስተር ካርላይል ከልዩ ቢሮው ገብቶ ሲሠራ ዋና ጸሐፊው
ሚስተር ዲል ገብቶ ባለጉዳይ ሊያነጋግረው እንደሚፈልግ ነገረው "
አሁን ሥራ ይዣለሁ : ማንንም ማነጋገር አልችልም
" ምነው እያወቅህ ..
ዲል ? አለው።
“ እንደዚያ ብነግረው : እጠብቃለሁ " አለኝ » ያ ካፒቴን ቶርን የሚባለው
ከጆን ሔርበርት ቤት ያረፈው እኮ ነው .
ሚስተር ካርላይል ቀና ብሎ ከዲል ጋር ተያዩና እሱንስ አነጋግረዋለሁ አስገባው አለው ።
የካፒቴን ጕዳይ ቀላል ነበር በየጊዜው ብዙ መኮንኖች እንደሚያደርጉት በዱቤ ዕዳ ምክንያት ክርክር ስለ ተነሣበት የሚስተር ካርላይልን የሕግ ምክር ለመጠየቅ ነበር "
ምክሩን ልሰጥህ እችላለሁ ነገር ግን የማንንም ጉዳይ ከማጥናቴ በፊት
ማንነት በደንብ ማወቅ አለብኝ " አባቴም አንድን ጉዳይ ከመቀበሉ
በፊት የባለ ጉዳዩን ትክክለኛ ሰው መሆንና የጉዳዩንም ሐቀኛ አነሣሥ ያጠና ነበር እኔም ከሱ ወርሼ በዚህ ዐይነት ነው የምሠራው "
“ ቤተሰቦቼም የታወቁ ናቸው " አለው ካፒቴን ቶርን
“ የኔ ጥያቄ የቤተሰብ ጥያቄ አይደለም » እኔ የቀን የጉልበት ሠራተኛም ሆነ
ለምኖ አዳሪ ቢመጣ ሐቀኛ ሰው መሆኑን በትክክል ካወቅሁ አነጋግረዋለሁ " ስለዚህ አሁንም ካንተ የምፈልገው ስለ ራስህና ስለ ጠባይህ ለማወቅ ነው
ታዲያ እኔ ጥሩ ሰው መሆኔን በምን ላሳምንሀ እችላለሁ ? አለው ካፒቴኑ
የጠበቃው ጥያቄ እንግዳ ቢሆንበትም በትሕትናውና በአቀራረቡ ተደፋፍሮ " አገሬን ማገልገል የጀመርኩት ካሥራ ስድስት ዓመቴ ጀምሬ ሲሆን የሥራ ጓደኞቼ በኔ ጠባይ ምንም የቅሬታ ነጥብ አግኝተውብኝ አያውቁም ከዚህ በተረፈ ጆን ሔርበርትን መጠየቅ ይቻላል ”
“ እስቲ በል ባለብኝ የሥራ ብዛት ምክንያት ጥብቅና ልቆምልህ አስቀድሜ
ቃል ልገባልህ ባልችልም ' ለጊዜው ማድረግ የምትችለውን ልነግርሀ እችላለሁ ” ካፒቴን ቶርን ችግሩን ገለጸለትና አስፈላጊውን ምክር ከሰጦው በኋላ ሌላ
ጨዋታ ያዙ " የዛሬ ዐሥር ዐመት ኢስት ሊን አልነበርክም ? አንድ ጊዜ እባቴ መጥተው ክደህ ነበር በኋላ ግን ከዚህ እንደ ነበርክ ደረስኩበት ” አለው
በርግጥ እንዲዛመት የማልፈልገው የግሌ ምክንያት ስለ ነበረኝ ነው እንጂ እሱስ ነበርኩ " አሁንም ካንተ አይለፍ እንጂ ብነግርህ ግድ የለኝም በዌስት ሊን ኣካባቢ ነበርኩ ያን ጊዜ የልጅነት ጠባይ ይዞኝ በሴት የተነሣ አንድ ነገር ተፈጠረ
ዛሬም በዚህ አካባቢ መኖሬ እንዲወራ ኣልፈልግም "
“ ገባኝ ” አለ ሚስተር ካርላይል የልቡ አመታት እየጨመረ “ ልጅቱ አፊ
ሆሊጆን የምትባል ነበረች "
“ አፊ ሆሊጆን ? እኔ እንደዚህ ያለ ስም በሕይወቴ ሰምቸ አላውቅም " "
በዚያን ዘመን አንድ አሳዛኝ ነገር መፈጸሙን አላወቅህም ? አልሰማህም ?
አሃ ! ቆይ እስቲ ያቺ አባቷ እንደ ተገደለ መጥፋቷን ቶም ሔርበርት የነገረኝ
እንደሆነች ?
“ አዎን ከገዛ ቤቱ ከልጁ ፊት የተገደለው ያባቴ ጸሐፊ ነበር ” አለው ሚስተር ካርላይል
“የገደለው ደግሞ የጀስቲስ ሔር ልጅ የዛያች ቆንጆይቱ የባርባራ ወንድም ትንሹ ሪቻርድ ሔር ነበር ይህን ነገር ብታነሳ አንድ ጊዜ ሰዎች የነገሩኝ ትዝ አለኝ
መጀመርያ ሔርበርት ቤት የመጣሁ ዕለት ማታ ጀስቲስ ሔርና ሌሎችም ትምባሆ ለማጤስ እዚያ መጥተው ነበር ያን ጊዜ ደግሞ ባባራን ካንተ ግቢ በር አይቻት ነበርና ቶም ሔርበርት ስለ ግድያው አጫወተኝ የሔርን ቤተሱብ ከባድ መከራ ነው
ያገኛቸው " ሚስ ሔርም በቂ ሀብትና ጥሩ መልክ እያላት ባል አግብታ ስሟን መለወጥ ሲገባት እስከ ዛሬ ባርባራ ሔር መባሏ በዚህ ምክንያት ይመስለኛል "
ምክንያቱ እንኳን እሱ አይደለም " ወንድሟ ነፍስ አጥፍቷል ቢባልም እሷን
ለማግባት የጠየቄ ብዙ ሰዎች እንዳሉ ዐውቃለሁ ስለዚህ ስሟን አታጉድፈው
ይኸን አባባልህን ዐርም ።
“እኔስ በዚህ አልንቃትም እንዲያውም ልጅቱ በጣም ደስ ትለኛለች " አለና ካፕቴን ቶርን ጫወታውን ቀጠለ “ እና ያቺ አፊ ከዚያ ወዲህ ወሬዋ ተሰምቶ አያውቅም ?
“ በጭራሽ ” አለ ሚስተር ካርላይል "ደህና አድርገህ ታውቃት ነበር አለው ሆነ ብሎ ።
“ እኔ ቶም ሔርበርት ስለሷ ሳይነግረኝ በፊት ስሟንም ሰምቸው አላውቅ ግን ለምንድነው የማውቃት መስዬ የታየሁህ ?
ሚስተር ካርላይል ' ሰውየው የሚናገረው እውነት ይሁን ውሸት ለማረጋገጥ በጣም ጓጓ "
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
ሳቤላ በባሏና በባርባራ ሔር ግንኙነት የነበራት ቅናት ፍራንሲዝ ሌቪሰን
ኢስት ሊን ከገባ ወዲህ ከምን ጊዜም የበለጠ ጨምሮ ታደሰባት ባርባራ በበኩሏ ሪቻርድ ባረጋገጠው መሠረት ወንጀሉን የፈጸመው ፍሬድሪክ ቶርን መሆኑን በማመን፡ የተሰወረው ምስጢር ገሃድ ሆኖ ወንድሟ ከወደቀበት ከባድ መከራ በፍርድ ነጻ ተለቆ ለማየት ከመጓጓቷ የተነሣ ልቧን ከመሳት አፋፍ ደርሳ ነበር ።በነገሩ ብታምንበትም ምንም ለማድረግ ኃይል አልነበራትም ከእንቅልፍ ይልቅ ቅዠት የበዛበት ሌሊት ዐልፎ በነጋ ቁጥር ' ' ምነው ዛሬ አንዳች የማረጋገጫ ነጥብ ባገኘሁ! ተጠርታም
ከሔርበርት ቤት ብዙ ጊዜ ተመላልሳለች የሚስተር ሔርበርት ሴት ልጆችም ባልንጀሮቿ ስለ ነበሩ ፡ ለዕረፍት ለመጣው ወንድማቸው ልዩ ዝግጅት አድር?ው ሲጠሯት ካፒቴን ቶርንን ብዙ ጊዜ አይታዋለች
እንዶዚህ በመስሉ አጋጣሚዎች ስለ ዐለፈው ታሪኩ አንዳንድ ነር ትለቃቅምና ያገኘችውን ይዛ ወደ ሚስተር ካርላይል ትሮጣለች ከቢሮው ስትሔድ ቶርን ያያት
እንደሆነ እንዳይነቃ በመፍራት ወዶ ኢስት ሊን ሔዳ አለበለዚያ ደሞ ወደ ቢሮ ሲሔድ ወይም ከቢሮ ሲመለስ ከመንገድ ጠብቃ ነበር የምታገኘው "ነገር ግን ! ይኸን ያህል የሚጠቅም ነገር ይዛ መጥታ አታውቅም » አንድ ቀን ማታ ቶርን ዱሮ
ዌስት ሊን እንደ ነበረ ልትነግረው መጣች " በሌላ ቀን ደግሞ ለይምሰል እመቤት ሳቤላን ለመጠየቅ መጣችና ሚስተር ካርይልን ለብቻው ልታነጋግረው እንደምትፈልግ ነገረችው " ተመራርተው ወጡና ኢያወሩ እስከ መናፈሻው በር አብሯት ሲሔድ ሁሉ የሳቤላ ቀናተኛ ዐይኖች ያዩዋቸዋል " ስለ ቶርን ትነግረው " የነበሩት ነጥቦች ሁሉ ጠንካራ አይደሉም እነሱንም ሚስተር ካርላይልም ቀደም ብሎ
ያውቃቸዋል " እሱ ግን መስማቱን ሳይገልጽላት በጉጉትና በስሜት ያዳምጣታል "
ሳቤላ ባሏና ባርባራ ሲገናኙ በዐይኗ አይታ ተናደደች ቁጠዋ ተቀስቅሶ የአእምሮዋ ሰላም ደፍርሶ ትትከነከናለች " ፍራንሊዝ ሌቪሰን ደግሞ እሷ ያላየቻችውን ግንኙነቶች እየተከታተለ ይነግራት ጀመር " ሚስተር ካርላይል ለጤና ይበጃል እያለ ይበልጡን ጊዜ ከቢሮ ወደ ቤት በእግሩ ይመላለስ ነበር " በሚስተር ሔር ቤት ሲያልፍ ባርባራ እየጠበቀችም ሆነ ባጋጣሚ ስታገኘው የቶርንን ነገር በምታነጋግረው ጊዜ ካፒቴን ሌቪሰን ቁጥቋጦ ለቁጥቋጦ እንደ እባብ እየተምለገለገ ሔዶ
ይመላከታቸውና እየጨማመረና እያጋነነ ለሳቤላ ይነግራት ጀመር "
ባርባራ ግን ስለ ሳቤላ ቅናት ምንም ነገር አታውቅም እሱም ሚስቱን እንደሚወድና ለሷም አንዲት የፍቅር ፊት አሳይቷት ስለማያውቅ ሳቤላ በሷ መቅናቷን ሰው ቢነግራት እንኳን በነጋሪዋ ከመሣቅ በቀር አታምንም ነበር
ዱሮ በፍቅር ትነድለት የነበረው ሁሉ ከሁኔታው ተረድታ ትታው' አሁን ካርላይል ዘንድ የሚያመላልሳት
የወንድሟ ጉዳይ ብቻ ሆኖ ነበር "
ኣንድ ቀን ጠዋት ሚስተር ካርላይል ከልዩ ቢሮው ገብቶ ሲሠራ ዋና ጸሐፊው
ሚስተር ዲል ገብቶ ባለጉዳይ ሊያነጋግረው እንደሚፈልግ ነገረው "
አሁን ሥራ ይዣለሁ : ማንንም ማነጋገር አልችልም
" ምነው እያወቅህ ..
ዲል ? አለው።
“ እንደዚያ ብነግረው : እጠብቃለሁ " አለኝ » ያ ካፒቴን ቶርን የሚባለው
ከጆን ሔርበርት ቤት ያረፈው እኮ ነው .
ሚስተር ካርላይል ቀና ብሎ ከዲል ጋር ተያዩና እሱንስ አነጋግረዋለሁ አስገባው አለው ።
የካፒቴን ጕዳይ ቀላል ነበር በየጊዜው ብዙ መኮንኖች እንደሚያደርጉት በዱቤ ዕዳ ምክንያት ክርክር ስለ ተነሣበት የሚስተር ካርላይልን የሕግ ምክር ለመጠየቅ ነበር "
ምክሩን ልሰጥህ እችላለሁ ነገር ግን የማንንም ጉዳይ ከማጥናቴ በፊት
ማንነት በደንብ ማወቅ አለብኝ " አባቴም አንድን ጉዳይ ከመቀበሉ
በፊት የባለ ጉዳዩን ትክክለኛ ሰው መሆንና የጉዳዩንም ሐቀኛ አነሣሥ ያጠና ነበር እኔም ከሱ ወርሼ በዚህ ዐይነት ነው የምሠራው "
“ ቤተሰቦቼም የታወቁ ናቸው " አለው ካፒቴን ቶርን
“ የኔ ጥያቄ የቤተሰብ ጥያቄ አይደለም » እኔ የቀን የጉልበት ሠራተኛም ሆነ
ለምኖ አዳሪ ቢመጣ ሐቀኛ ሰው መሆኑን በትክክል ካወቅሁ አነጋግረዋለሁ " ስለዚህ አሁንም ካንተ የምፈልገው ስለ ራስህና ስለ ጠባይህ ለማወቅ ነው
ታዲያ እኔ ጥሩ ሰው መሆኔን በምን ላሳምንሀ እችላለሁ ? አለው ካፒቴኑ
የጠበቃው ጥያቄ እንግዳ ቢሆንበትም በትሕትናውና በአቀራረቡ ተደፋፍሮ " አገሬን ማገልገል የጀመርኩት ካሥራ ስድስት ዓመቴ ጀምሬ ሲሆን የሥራ ጓደኞቼ በኔ ጠባይ ምንም የቅሬታ ነጥብ አግኝተውብኝ አያውቁም ከዚህ በተረፈ ጆን ሔርበርትን መጠየቅ ይቻላል ”
“ እስቲ በል ባለብኝ የሥራ ብዛት ምክንያት ጥብቅና ልቆምልህ አስቀድሜ
ቃል ልገባልህ ባልችልም ' ለጊዜው ማድረግ የምትችለውን ልነግርሀ እችላለሁ ” ካፒቴን ቶርን ችግሩን ገለጸለትና አስፈላጊውን ምክር ከሰጦው በኋላ ሌላ
ጨዋታ ያዙ " የዛሬ ዐሥር ዐመት ኢስት ሊን አልነበርክም ? አንድ ጊዜ እባቴ መጥተው ክደህ ነበር በኋላ ግን ከዚህ እንደ ነበርክ ደረስኩበት ” አለው
በርግጥ እንዲዛመት የማልፈልገው የግሌ ምክንያት ስለ ነበረኝ ነው እንጂ እሱስ ነበርኩ " አሁንም ካንተ አይለፍ እንጂ ብነግርህ ግድ የለኝም በዌስት ሊን ኣካባቢ ነበርኩ ያን ጊዜ የልጅነት ጠባይ ይዞኝ በሴት የተነሣ አንድ ነገር ተፈጠረ
ዛሬም በዚህ አካባቢ መኖሬ እንዲወራ ኣልፈልግም "
“ ገባኝ ” አለ ሚስተር ካርላይል የልቡ አመታት እየጨመረ “ ልጅቱ አፊ
ሆሊጆን የምትባል ነበረች "
“ አፊ ሆሊጆን ? እኔ እንደዚህ ያለ ስም በሕይወቴ ሰምቸ አላውቅም " "
በዚያን ዘመን አንድ አሳዛኝ ነገር መፈጸሙን አላወቅህም ? አልሰማህም ?
አሃ ! ቆይ እስቲ ያቺ አባቷ እንደ ተገደለ መጥፋቷን ቶም ሔርበርት የነገረኝ
እንደሆነች ?
“ አዎን ከገዛ ቤቱ ከልጁ ፊት የተገደለው ያባቴ ጸሐፊ ነበር ” አለው ሚስተር ካርላይል
“የገደለው ደግሞ የጀስቲስ ሔር ልጅ የዛያች ቆንጆይቱ የባርባራ ወንድም ትንሹ ሪቻርድ ሔር ነበር ይህን ነገር ብታነሳ አንድ ጊዜ ሰዎች የነገሩኝ ትዝ አለኝ
መጀመርያ ሔርበርት ቤት የመጣሁ ዕለት ማታ ጀስቲስ ሔርና ሌሎችም ትምባሆ ለማጤስ እዚያ መጥተው ነበር ያን ጊዜ ደግሞ ባባራን ካንተ ግቢ በር አይቻት ነበርና ቶም ሔርበርት ስለ ግድያው አጫወተኝ የሔርን ቤተሱብ ከባድ መከራ ነው
ያገኛቸው " ሚስ ሔርም በቂ ሀብትና ጥሩ መልክ እያላት ባል አግብታ ስሟን መለወጥ ሲገባት እስከ ዛሬ ባርባራ ሔር መባሏ በዚህ ምክንያት ይመስለኛል "
ምክንያቱ እንኳን እሱ አይደለም " ወንድሟ ነፍስ አጥፍቷል ቢባልም እሷን
ለማግባት የጠየቄ ብዙ ሰዎች እንዳሉ ዐውቃለሁ ስለዚህ ስሟን አታጉድፈው
ይኸን አባባልህን ዐርም ።
“እኔስ በዚህ አልንቃትም እንዲያውም ልጅቱ በጣም ደስ ትለኛለች " አለና ካፕቴን ቶርን ጫወታውን ቀጠለ “ እና ያቺ አፊ ከዚያ ወዲህ ወሬዋ ተሰምቶ አያውቅም ?
“ በጭራሽ ” አለ ሚስተር ካርላይል "ደህና አድርገህ ታውቃት ነበር አለው ሆነ ብሎ ።
“ እኔ ቶም ሔርበርት ስለሷ ሳይነግረኝ በፊት ስሟንም ሰምቸው አላውቅ ግን ለምንድነው የማውቃት መስዬ የታየሁህ ?
ሚስተር ካርላይል ' ሰውየው የሚናገረው እውነት ይሁን ውሸት ለማረጋገጥ በጣም ጓጓ "
👍15😁2
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የእንጀራ አባቴ
በዚያ ፀደይ ክሪስ ታመመ አፉ አካባቢ አረንጓዴ መሰለና በየደቂቃው
ያስመልሰው ጀመር። ከመታጠቢያ ቤት ወጥቶ እየተንገዳገደ አልጋ ላይ ወደቀ። የስነ አካል ጥናት ለማንበብ እየሞከረ ግን በራሱ ተናዶ ወደጎን አሽቀነጠረው። “የሆነ የበላሁት ነገር መሆን አለበት" ሲል ተነጫነጨ።
ክሪስ ብቻህን ልተውህ አልፈልግም” አልኩ ከእንጨት የተሰራውን ቁልፍ
ወደ ቁልፍ ቀዳዳው ለማስገባት እያዘጋጀሁ።
“ተመልከቺ ካቲ!” ሲል ጮኸ “በራስሽ ሁለት እግሮች መቆም የምትማሪበት ጊዜ ነው: በእያንዳንዱ ደቂቃ አጠገብሽ እንድሆን አትፈልጊ! የእናታችን ችግር
ያ ነበር። ሁልጊዜ የምትደገፍበት ሰው አጠገቧ እንዲኖር ታስባለች: በራስሽ ላይ ተደገፊ እሺ ካቲ… ሁልጊዜም!”
ፍርሀት ዘሎ ልቤ ውስጥ ገባና በአይኖቼ ፈሰሰ። አየኝና በእርጋታ “እኔ ደህና
ነኝ። እውነቴን ነው ራሴን መንከባከብ እችላለሁ: ካቲ ገንዘቡ ያስፈልገናል።
ሌላ ዕድል ላይኖረን ስለሚችል ብቻሽንም ቢሆን ሂጂ።
ወደ እሱ አልጋ ሮጩ ተመለስኩና በጉልበቴ ተንበርክኬ ፊቴን ደረቱ ላይ
አደረግኩ። በደግነት ፀጉሬን ዳሰሰኝ፡ “እውነት ካቲ፣ ደህና እሆናለሁ፤ ልታለቅሺበት የሚገባ አይደለም: ግን ሊገባሽ የሚገባው ነገር አንዳችን ላይ ምንም ነገር ቢፈጠር የቀረነው መንትዮቹን ከዚህ ማውጣት አለበት።”
“እንደዚህ አይነት ነገሮች አትናገር!” ጮህኩበት። እንደሚሞት ማሰቡ ውስጤን አሳመመኝ።
"ካቲ… አሁን እንድትሄጂ እፈልጋለሁ: ተነሺ ራስሽን አስገድጂ! እዚያ
ስትደርሺ ደግሞ ባለአንዳንድና ባለ አምስት ኖቶች ብቻ ውሰጂ እንጂ ትልልቆቹን እንዳትነኪ የእንጀራ አባታችን ኪሱ ውስጥ የሚጥላቸውን ሳንቲሞች ግን ሁሉንም ውሰጂ ከልብስ ማስቀመጫው ሳጥን ጀርባ ሳንቲሞች የሞሉበት
አንድ ቆርቆሮ ያስቀምጣሉ፡ ከእነሱ ዝገኚ”።
የገረጣና የደከመው ይመስላል። በዚያ ላይ ከስቷል: ደህና ሳይሆን ትቼው መውጣት እያስጠላኝ በፍጥነት ጉንጩን ሳም አደረግኩት። ወደተኙት መንትዮች አየት አድርጌ ከእንጨት የተሰራውን ቁልፍ ይዤ ወደ በሩ ተጣደፍኩ። “እወድሀለሁ ክሪስቶፈር” አልኩት በሩን ከመክፈቴ በፊት።
“እኔም እወድሻለሁ ካተሪን መልካም አደን” አለኝ፡
በአየር ላይ ሳምኩትና ወጥቼ በሩን ዘጋሁና ቆለፍኩት። እናቴ ክፍል ገብቶ መስረቅ አደጋ የለውም። እናታችን እሷና ባሏ ከመንገዱ በታች ያለ ጓደኛቸው ግብዣ ላይ መገኘት እንዳለባቸው የነገረችን ዛሬ ከሰአት በኋላ ነበር:
ኮሪደሩን አቋርጬ ስሄድ ለራሴ እያሰብኩ የነበረው ቢያንስ አንድ ባለ ሀያና
አንድ ባለ አስር ኖቶች መስረቅ እንዳለብኝ ነበር: የሆነ ሰው እንዳያስተውል
አደርጋለሁ። ምናልባትም ከእናታችን ጌጣጌጦች የተወሰኑ እሰርቃለሁ፡
ጌጣጌጦች አቅም ሊኖራቸው ይችላል ልክ እንደ ገንዘብ፤ ምናልባትም በተሻለ።
ሁሉም ስራ ነው፤ ሁሉም ቆራጥነት። የሽልማት ክፍሉን ለማየት ጊዜ ማባከን አልፈለግኩም ቀጥታ ወደ እናታችን መኝታ ክፍል አመራሁ። አሁን አራት
ሰዓት ነው፡ በጊዜ በሶስት ሰዓት የምትተኛውን አያትየውን እንደማላያት
አውቄያለሁ በጀግና የመተማመን ቆራጥነት ወደ ክፍሎቿ በሚያስገቡት በሮች ገባሁና በፀጥታ ዘጋኋቸው:: አንድ ደብዛዛ መብራት ብቻ በርቷል። በአብዛኛው ክፍሎቿ ውስጥ ያሉትን መብራቶች አብርታ ትተዋቸዋለች: አንዳንዴ ደግሞ
አንዱን ብቻ አብርታ እንደምትተወው ክሪስ ነግሮኛል። አሁን ለእናታችን
ገንዘብ ምኗ ነው?
እያመነታሁና እርግጠኛ ባለመሆን በሩ ጋ እንደቆምኩ ዙሪያውን ስመለከት በፍርሀት ደነዘዝኩ የእናታችን አዲስ ባል ወንበሩ ላይ ረጅም እግሮቹን ዘርግቶና ቁርጭምጭሚቱ
ጋር አጣምሮ ተዘርግቷል: ቀጥታ ፊት ለፊቱ ነኝ፡ አጭር የሚያሳይ የሌሊት ልብስና ከስር ደግሞ ከእሱ ጋር የሚመሳሰል ፓንት ለብሻለሁ፡ ማን እንደሆንኩና ሳልጠራ መኝታ ቤት ውስጥ ምን እያደረግኩ እንደሆነ ለማወቅ እስኪያጓራ ልቤ በአበደ አይነት እየመታ እጠብቃለሁ።
ግን አልተናገረም ጥቁር ቶክሲዶ ጠርዙ ላይ ወደታች ከሚወርድ ጥቁር ጌጥ ያለው ሮዝ ሸሚዝ
ጋር ለብሷል። አልጮኸም. አልጠየቀም ምክንያቱም እያንቀላፋ ነበር። ፊቴን አዙሬ ልመለስ ነበር ግን ይነቃና ያየኛል ብዬ ፈራሁ
መቼም መጓጓት ስራዬ ሆኗል በደንብ ልመለከተው ቀረብ አልኩ፡ ልነካው
እስከምችል ወንበሩ ድረስ ለመጠጋት ደፈርኩ እጄን ኪሱ ገብቼ መስረቅ
የምችልበት ቅርበት ላይ ሆንኩ ግን አላደረግኩትም፡
እንቅልፍ የወሰደው መልከመልካም ፊቱን ስመለከት፣ መስረቅ ጭንቅላቴ ውስጥ የመጣው የመጨረሻ ሀሳብ ነበር፡ አሁን የተገለጠውን በጣም የቀረብኩትን የእናቴን ተወዳጅ ባርትን በማየቴ ተደንቄያለሁ፡ የተወሰኑ ጊዜያት በሩቅ አይቼዋለሁ: በመጀመሪያ የገና ግብዣው ምሽት ሌላው ደግሞ ደረጃው አጠገብ እናታችን እጇን እንድታጠልቅ ኮት ይዞላት ማጅራቷና ጆሮዋ
ስር ሲስማትና ፈገግ እንድትል የሚያደርግ የሆነ ነገር በጆሮዋ ሲያንሾካሹክላት
እና ከበር ከመውጣታቸው በፊት ወደ ራሱ ጎትቶ ደረቱ ላይ ሲያስደግፋት
አይቼዋለሁ።
አዎ አዎ አይቼዋለሁ... እና ደግሞ ስለሱ ብዙ ሰምቼያለሁ፡ እህቶቹ የት
እንደሚኖሩ አውቃለሁ፡ የት እንደተወለደ፣ የት እንደተማረ ሁሉ አውቃለሁ።
አሁን እያየሁት ላለሁት ግን ማንም እንድዘጋጅ አላደረገኝም:
እንዴት እናቴ? ማፈር አለብሽ! ይህ ሰው በእድሜ ካንቺ ያንሳል በብዙ
አመታት ያንሳል! ግን አልነገረችንም ሚስጥር ነበር። እንደዚህ አይነት
አስፈላጊ ሚስጥር እንዴት መደበቅ እንደቻለች! ማንኛዋም ሴት የምትፈልገው አይነት ወንድ ነው፡ እና ብትወደውና ብታመልከው ምንም አይገርምም። የተለየ ግርማ ሞገስ ባለው ሁኔታ ተጋድሞ ስመለከተው ፍቅር ሲሰሩ
ኃይለኛና በስሜት የተሞላ እንደሚሆንላት ገመትኩ፡
ወንበር ላይ ተቀምጦ የሚያንቀላፋውን ይህንን ሰው መጥላት ፈለግኩ
ግን አልቻልኩም: እንቅልፍ ወስዶት እንኳን ቆንጆ ነውና ልቤ በፍጥነት እንዲመታ አደረገው። ባርትሎሚዮ ዊንስሎ ሳያውቀው በእንቅልፍ ልቡ ለእኔ የአድናቆት ምላሽ
በመስጠት አይነት ፈገግ አለ፡ እንደ ዶክተሮችና እንደ ክሪስ ሁሉንም ነገር
ከሚያውቁ ሰዎች አንዱ ነው ጠበቃ: እርግጠኛ ነኝ የሆነ በተለየ ሁኔታ ደስ የሚያሰኝ ነገር አይቶና ሞክሮ ያውቃል፡ በተከደኑ አይኖቹ ስር ያለው
ምን ይሆን? አይኖቹ ሰማያዊ ይሆኑ ወይም ቡናማ ማወቅ ፈለግኩ። ሰውነቱ ቀጭን፣ ጠንካራና ጡንቻማ ነው: ከንፈሮቹ አጠገብ ከላይ ወደታች የተሰመረ የሚመስል በእንቅልፍ ልቡ ፈገግ ሲል እየመጣ የሚመለስ ስርጉደት አለው::
ትልቅ የጋብቻ ቀለበት አጥልቋል። አይነቱን እናቴ ጣት ላይ አይቼዋለሁ:
በቀኝ እጁ አመልካች ጣት ላይ ብዙ ብርሀን በሌለበት እንኳን የሚያንፀባርቅ
የአልማዝ ቀለበት አለው ትንሽዋ ጣቱ ላይ ትምህርት ቤት ለሽልማት የሚሰጥ
የወንድማማችነት ቀለበት አድርጓል። ረጃጅም ጣቶቹ በደንብ የተፀዱና ልክ
እንደኔ ጥፍሮች የሚያንፀባርቁ አራት ማዕዘን ጥፍሮች አሏቸው
ረጅም ነው: ይህንን አስቀድሜ አውቃለሁ፡ ከሁሉ ነገር በጣም ደስ ያለኝ ስሜት የሚቀሰቅሱ ከፂሙ በታች ያሉት ማራኪ hንፈሮቹ ናቸው: በእነዚህ
ቅርፃቸው በሚያምር ማራኪ ከንፈሮቹ እናታችንን ሁሉም ቦታ ይስሟታል። ያ የወሲብ ደስታ ያለበት መፅሀፍ ትልልቅ ሰዎች እርቃናቸውን ሲሆኑ ምን ስሜት እንደሚሰጣቸው በሚገባ አስተምሮኛል።
ድንገት ያ ጥቁር ፂሙ ይኮረኩር እንደሆነ ለማየት እሱን የመሳም ግፊት
አደረብኝ:፡ በዚያውም ምንም አይነት የደም ዝምድና የሌለው እንግዳ መሳም ምን ስሜት እንደሚያሳድር ማወቅ ፈልጌያለሁ:
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የእንጀራ አባቴ
በዚያ ፀደይ ክሪስ ታመመ አፉ አካባቢ አረንጓዴ መሰለና በየደቂቃው
ያስመልሰው ጀመር። ከመታጠቢያ ቤት ወጥቶ እየተንገዳገደ አልጋ ላይ ወደቀ። የስነ አካል ጥናት ለማንበብ እየሞከረ ግን በራሱ ተናዶ ወደጎን አሽቀነጠረው። “የሆነ የበላሁት ነገር መሆን አለበት" ሲል ተነጫነጨ።
ክሪስ ብቻህን ልተውህ አልፈልግም” አልኩ ከእንጨት የተሰራውን ቁልፍ
ወደ ቁልፍ ቀዳዳው ለማስገባት እያዘጋጀሁ።
“ተመልከቺ ካቲ!” ሲል ጮኸ “በራስሽ ሁለት እግሮች መቆም የምትማሪበት ጊዜ ነው: በእያንዳንዱ ደቂቃ አጠገብሽ እንድሆን አትፈልጊ! የእናታችን ችግር
ያ ነበር። ሁልጊዜ የምትደገፍበት ሰው አጠገቧ እንዲኖር ታስባለች: በራስሽ ላይ ተደገፊ እሺ ካቲ… ሁልጊዜም!”
ፍርሀት ዘሎ ልቤ ውስጥ ገባና በአይኖቼ ፈሰሰ። አየኝና በእርጋታ “እኔ ደህና
ነኝ። እውነቴን ነው ራሴን መንከባከብ እችላለሁ: ካቲ ገንዘቡ ያስፈልገናል።
ሌላ ዕድል ላይኖረን ስለሚችል ብቻሽንም ቢሆን ሂጂ።
ወደ እሱ አልጋ ሮጩ ተመለስኩና በጉልበቴ ተንበርክኬ ፊቴን ደረቱ ላይ
አደረግኩ። በደግነት ፀጉሬን ዳሰሰኝ፡ “እውነት ካቲ፣ ደህና እሆናለሁ፤ ልታለቅሺበት የሚገባ አይደለም: ግን ሊገባሽ የሚገባው ነገር አንዳችን ላይ ምንም ነገር ቢፈጠር የቀረነው መንትዮቹን ከዚህ ማውጣት አለበት።”
“እንደዚህ አይነት ነገሮች አትናገር!” ጮህኩበት። እንደሚሞት ማሰቡ ውስጤን አሳመመኝ።
"ካቲ… አሁን እንድትሄጂ እፈልጋለሁ: ተነሺ ራስሽን አስገድጂ! እዚያ
ስትደርሺ ደግሞ ባለአንዳንድና ባለ አምስት ኖቶች ብቻ ውሰጂ እንጂ ትልልቆቹን እንዳትነኪ የእንጀራ አባታችን ኪሱ ውስጥ የሚጥላቸውን ሳንቲሞች ግን ሁሉንም ውሰጂ ከልብስ ማስቀመጫው ሳጥን ጀርባ ሳንቲሞች የሞሉበት
አንድ ቆርቆሮ ያስቀምጣሉ፡ ከእነሱ ዝገኚ”።
የገረጣና የደከመው ይመስላል። በዚያ ላይ ከስቷል: ደህና ሳይሆን ትቼው መውጣት እያስጠላኝ በፍጥነት ጉንጩን ሳም አደረግኩት። ወደተኙት መንትዮች አየት አድርጌ ከእንጨት የተሰራውን ቁልፍ ይዤ ወደ በሩ ተጣደፍኩ። “እወድሀለሁ ክሪስቶፈር” አልኩት በሩን ከመክፈቴ በፊት።
“እኔም እወድሻለሁ ካተሪን መልካም አደን” አለኝ፡
በአየር ላይ ሳምኩትና ወጥቼ በሩን ዘጋሁና ቆለፍኩት። እናቴ ክፍል ገብቶ መስረቅ አደጋ የለውም። እናታችን እሷና ባሏ ከመንገዱ በታች ያለ ጓደኛቸው ግብዣ ላይ መገኘት እንዳለባቸው የነገረችን ዛሬ ከሰአት በኋላ ነበር:
ኮሪደሩን አቋርጬ ስሄድ ለራሴ እያሰብኩ የነበረው ቢያንስ አንድ ባለ ሀያና
አንድ ባለ አስር ኖቶች መስረቅ እንዳለብኝ ነበር: የሆነ ሰው እንዳያስተውል
አደርጋለሁ። ምናልባትም ከእናታችን ጌጣጌጦች የተወሰኑ እሰርቃለሁ፡
ጌጣጌጦች አቅም ሊኖራቸው ይችላል ልክ እንደ ገንዘብ፤ ምናልባትም በተሻለ።
ሁሉም ስራ ነው፤ ሁሉም ቆራጥነት። የሽልማት ክፍሉን ለማየት ጊዜ ማባከን አልፈለግኩም ቀጥታ ወደ እናታችን መኝታ ክፍል አመራሁ። አሁን አራት
ሰዓት ነው፡ በጊዜ በሶስት ሰዓት የምትተኛውን አያትየውን እንደማላያት
አውቄያለሁ በጀግና የመተማመን ቆራጥነት ወደ ክፍሎቿ በሚያስገቡት በሮች ገባሁና በፀጥታ ዘጋኋቸው:: አንድ ደብዛዛ መብራት ብቻ በርቷል። በአብዛኛው ክፍሎቿ ውስጥ ያሉትን መብራቶች አብርታ ትተዋቸዋለች: አንዳንዴ ደግሞ
አንዱን ብቻ አብርታ እንደምትተወው ክሪስ ነግሮኛል። አሁን ለእናታችን
ገንዘብ ምኗ ነው?
እያመነታሁና እርግጠኛ ባለመሆን በሩ ጋ እንደቆምኩ ዙሪያውን ስመለከት በፍርሀት ደነዘዝኩ የእናታችን አዲስ ባል ወንበሩ ላይ ረጅም እግሮቹን ዘርግቶና ቁርጭምጭሚቱ
ጋር አጣምሮ ተዘርግቷል: ቀጥታ ፊት ለፊቱ ነኝ፡ አጭር የሚያሳይ የሌሊት ልብስና ከስር ደግሞ ከእሱ ጋር የሚመሳሰል ፓንት ለብሻለሁ፡ ማን እንደሆንኩና ሳልጠራ መኝታ ቤት ውስጥ ምን እያደረግኩ እንደሆነ ለማወቅ እስኪያጓራ ልቤ በአበደ አይነት እየመታ እጠብቃለሁ።
ግን አልተናገረም ጥቁር ቶክሲዶ ጠርዙ ላይ ወደታች ከሚወርድ ጥቁር ጌጥ ያለው ሮዝ ሸሚዝ
ጋር ለብሷል። አልጮኸም. አልጠየቀም ምክንያቱም እያንቀላፋ ነበር። ፊቴን አዙሬ ልመለስ ነበር ግን ይነቃና ያየኛል ብዬ ፈራሁ
መቼም መጓጓት ስራዬ ሆኗል በደንብ ልመለከተው ቀረብ አልኩ፡ ልነካው
እስከምችል ወንበሩ ድረስ ለመጠጋት ደፈርኩ እጄን ኪሱ ገብቼ መስረቅ
የምችልበት ቅርበት ላይ ሆንኩ ግን አላደረግኩትም፡
እንቅልፍ የወሰደው መልከመልካም ፊቱን ስመለከት፣ መስረቅ ጭንቅላቴ ውስጥ የመጣው የመጨረሻ ሀሳብ ነበር፡ አሁን የተገለጠውን በጣም የቀረብኩትን የእናቴን ተወዳጅ ባርትን በማየቴ ተደንቄያለሁ፡ የተወሰኑ ጊዜያት በሩቅ አይቼዋለሁ: በመጀመሪያ የገና ግብዣው ምሽት ሌላው ደግሞ ደረጃው አጠገብ እናታችን እጇን እንድታጠልቅ ኮት ይዞላት ማጅራቷና ጆሮዋ
ስር ሲስማትና ፈገግ እንድትል የሚያደርግ የሆነ ነገር በጆሮዋ ሲያንሾካሹክላት
እና ከበር ከመውጣታቸው በፊት ወደ ራሱ ጎትቶ ደረቱ ላይ ሲያስደግፋት
አይቼዋለሁ።
አዎ አዎ አይቼዋለሁ... እና ደግሞ ስለሱ ብዙ ሰምቼያለሁ፡ እህቶቹ የት
እንደሚኖሩ አውቃለሁ፡ የት እንደተወለደ፣ የት እንደተማረ ሁሉ አውቃለሁ።
አሁን እያየሁት ላለሁት ግን ማንም እንድዘጋጅ አላደረገኝም:
እንዴት እናቴ? ማፈር አለብሽ! ይህ ሰው በእድሜ ካንቺ ያንሳል በብዙ
አመታት ያንሳል! ግን አልነገረችንም ሚስጥር ነበር። እንደዚህ አይነት
አስፈላጊ ሚስጥር እንዴት መደበቅ እንደቻለች! ማንኛዋም ሴት የምትፈልገው አይነት ወንድ ነው፡ እና ብትወደውና ብታመልከው ምንም አይገርምም። የተለየ ግርማ ሞገስ ባለው ሁኔታ ተጋድሞ ስመለከተው ፍቅር ሲሰሩ
ኃይለኛና በስሜት የተሞላ እንደሚሆንላት ገመትኩ፡
ወንበር ላይ ተቀምጦ የሚያንቀላፋውን ይህንን ሰው መጥላት ፈለግኩ
ግን አልቻልኩም: እንቅልፍ ወስዶት እንኳን ቆንጆ ነውና ልቤ በፍጥነት እንዲመታ አደረገው። ባርትሎሚዮ ዊንስሎ ሳያውቀው በእንቅልፍ ልቡ ለእኔ የአድናቆት ምላሽ
በመስጠት አይነት ፈገግ አለ፡ እንደ ዶክተሮችና እንደ ክሪስ ሁሉንም ነገር
ከሚያውቁ ሰዎች አንዱ ነው ጠበቃ: እርግጠኛ ነኝ የሆነ በተለየ ሁኔታ ደስ የሚያሰኝ ነገር አይቶና ሞክሮ ያውቃል፡ በተከደኑ አይኖቹ ስር ያለው
ምን ይሆን? አይኖቹ ሰማያዊ ይሆኑ ወይም ቡናማ ማወቅ ፈለግኩ። ሰውነቱ ቀጭን፣ ጠንካራና ጡንቻማ ነው: ከንፈሮቹ አጠገብ ከላይ ወደታች የተሰመረ የሚመስል በእንቅልፍ ልቡ ፈገግ ሲል እየመጣ የሚመለስ ስርጉደት አለው::
ትልቅ የጋብቻ ቀለበት አጥልቋል። አይነቱን እናቴ ጣት ላይ አይቼዋለሁ:
በቀኝ እጁ አመልካች ጣት ላይ ብዙ ብርሀን በሌለበት እንኳን የሚያንፀባርቅ
የአልማዝ ቀለበት አለው ትንሽዋ ጣቱ ላይ ትምህርት ቤት ለሽልማት የሚሰጥ
የወንድማማችነት ቀለበት አድርጓል። ረጃጅም ጣቶቹ በደንብ የተፀዱና ልክ
እንደኔ ጥፍሮች የሚያንፀባርቁ አራት ማዕዘን ጥፍሮች አሏቸው
ረጅም ነው: ይህንን አስቀድሜ አውቃለሁ፡ ከሁሉ ነገር በጣም ደስ ያለኝ ስሜት የሚቀሰቅሱ ከፂሙ በታች ያሉት ማራኪ hንፈሮቹ ናቸው: በእነዚህ
ቅርፃቸው በሚያምር ማራኪ ከንፈሮቹ እናታችንን ሁሉም ቦታ ይስሟታል። ያ የወሲብ ደስታ ያለበት መፅሀፍ ትልልቅ ሰዎች እርቃናቸውን ሲሆኑ ምን ስሜት እንደሚሰጣቸው በሚገባ አስተምሮኛል።
ድንገት ያ ጥቁር ፂሙ ይኮረኩር እንደሆነ ለማየት እሱን የመሳም ግፊት
አደረብኝ:፡ በዚያውም ምንም አይነት የደም ዝምድና የሌለው እንግዳ መሳም ምን ስሜት እንደሚያሳድር ማወቅ ፈልጌያለሁ:
👍47❤3😁2🔥1
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ኤዲ ዲኪን ራሱን ለመቆጣጠር ቢሞክርም ክዳኑ ተዘግቶ እንደሚንተከተክ ጀበና ሆኗል፡ በጭንቀት ሊፈነዳ ምንም አልቀረውም፡፡ ላቡ
አሁንም አሁንም ችፍ ይላል፡ ጨጓራው እየተቃጠለ በመሆኑ ሰውነቱ
እረፍት አጣ፡፡ ቀልቡን ሰብስቦ መስራት አልቻለም፡፡
ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ የእሱ ፈረቃ ያበቃል ወደ መውጫው ሰዓት ላይ የሀሰት የነዳጅ ፍላጎት መጠን አስልቶ በሰንጠረዡ ላይ አሰፈረ።
ካፒቴኑ ጉዞውን
ለማጠናቀቅ የሚያስችል በቂ ነዳጅ ያለው
ለማስመሰልና ወደ ኋላ እመለሳለሁ እንዳይል የአይሮፕላኑን የነዳጅ ፍጆታ
ፍላጎት መጠን አሳንሶ አስልቶ ነበር፡፡ የእሱ ተተኪ የሆነው ሚኪ ፊን ሲመጣ ልዩነቱን እንዳያውቅ የፍጆታ መጠኑን ከፍ አድርጎ በማስላት አካካሰው፡፡ የነዳጅ ፍጆታ መጠን በወጣ ገባነት መለዋወጡን ሚኪ ሲያይ ምን ተፈጠረ ብሎ መጠየቁ አይቀርም፡፡ ኤዲም ይህ የሆነው በወጀቡ ምክንያት ነው ሊለው ተዘጋጅቷል፡፡ የሆነ ሆኖ አሁን ሚኪ ምን እንደሚል ሳይሆን ያስጨነቀው፣ አዕምሮውን የውጥር የያዘው አይሮፕላኑ ኒውፋውንድ ላንድ (ካናዳ) ሳይደርስ ነዳጅ ይጨርስ ይሆን የሚለው ሃሳብ ነው፡፡
የበረራ ህጉ መያዝ ያለበትን መጠባበቂያ የነዳጅ መጠን ቢያስቀምጥም
አይሮፕላኑ የራሱ የሆነ ዝቅተኛ የነዳጅ ፍጆታ መጠን ደንብ የለውም:
አይሮፕላኑም ከአቅም በላይ ለሆነ ችግር የመጠባበቂያ ነዳጅ የለውም::በነዳጅ ችግር ምክንያት አንድ ችግር ቢከሰት አይሮፕላኑ ያለ ጥርጥር ማዕበል በበዛበት አትላንቲክ ውቂያኖስ ውስጥ መውደቁ አይቀርም፡፡ ከወደቀ
ደግሞ በትንሽ ደቂቃ ውስጥ ስለሚሰምጥ ለወሬ ነጋሪ እንኳን የሚተርፍ
የለም፡፡
ሚኪ እንደወትሮው ነቃ ብሎና ለስራ ተነሳስቶ ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት
ሲል ደረሰ፡፡ ‹‹ያለን ነዳጅ አነስተኛ መሆኑን ለካፒቴኑ ነግሬያለሁ›› አለው
ኤዲ፡፡
ሚኪም ያለው ነገር ብዙም ስሜት እንዳልሰጠው ሁሉ ራሱን በማነቃነቅ ብቻ መረዳቱን ገለፀለትና ባትሪውን አነሳ፡፡ የመጀመሪያ ስራው የአይሮፕላኑ አራት ሞተሮች በዓይን መቃኘት ነው፡፡
ኤዲ ሚኪን ባለበት ቦታ ትቶ ወደ ተሳፋሪዎች ክፍል አመራ፡ ረዳት.ካፒቴኑ ጆኒ ዶት ናቪጌተሩ ጃክ አሽፎርድና ሬዲዮ ኦፕሬተሩ ቤን ቶምስን ተከትለውታል፡፡ ጃክ ለራሱ ሳንድዊች ሊያዘጋጅ ወደ ኩሽና ሄደ፡፡ ኤዲ ምግብ መብላት አይደለም ምግብ ሲያይ ሊያስታውከው ስለሚደርስ አንድ ሲኒ ቡና ብቻ ጠጣ
ስራ በሌለው ሰዓት ባለቤቱ ካሮል አን በነዚያ አፋኞች መዳፍ ስር መሆኗ ብቻ ነው አዕምሮው ውስጥ የሚመጣው፡፡
አሁን በአሜሪካ ሜይን ስቴት ውስጥ ሰዓቱ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በመሆኑ ጨለማ ነው፡፡ ይሄን ጊዜ ካሮል አን ከመንገላታት ብዛት ዝላና ልቧ
ተሰብሮ ቁጭ ብላ ይሆናል፡፡ ነፍሰ ጡር ከሆነች ወዲህ በጊዜ ነው
የምትተኛው፡ ታዲያ እንድትተኛ ይፈቅዱላት ይሆን? መተኛት ቀርቶ
ጎኗን የምታሳርፍበት ቦታ ቢሰጧት ጥሩ ነበር፡፡
ምሽቱ እየገፋ ሲሄድ ሚስቱን ያገቷት ወሮበሎች ሌላ ክፉ ነገር ያውጠነጥኑ ይሆን? ሲል መጨነቅ ጀመረ፡፡
ወጀቡ እንደገና ተነሳ፡፡
አይሮፕላኑ መናጡ ባሰበት፡ በማዕበል ላይ የሚጓዝ መርከብ መስሏል፡ ግዙፍ አይሮፕላን አንዴ ከፍ እያለ አንዴ ዝቅ እያለ በንፋስ ወዲህ ወዲያ የተንገላታ ይጓዛል። ተሳፋሪዎቹ ስጋት ገብቷቸው ከእንቅልፋቸው ተነሱ አስተናጋጁንም ይጣሩ ጀመር፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ሆዳቸው ታውኮ ወደ
መጸዳጃ ክፍል ይሮጣሉ አስተናጋጆቹም ወደ ተሳፋሪዎቹ ተራወጡ፡
ኤዲ ቡና ለመጠጣት ሲሄድ ቶም ሉተር ፊቱ መጥቶ ድቅን አለ፡፡ሉተር በአይሮፕላኑ መናወጥ ደንግጦ ፊቱ አመድ መስሏል፡ ሰውነቱ በላብ
ርሷል፡ ኤዲም ጅንን ብሎ ያየዋል፡፡ ቶምን ጉሮሮውን ፈጥርቆ ሊይዘው ትንሽ ነበር የቀረው፤ ነገር ግን ንዴቱን ውጦ ዝም አለ፡፥
‹‹ይሄ ግን የተለመደ ነው?›› ሲል ጠየቀ ቶም በፍርሃት፡
ኤዲ ያለ ምንም ሀዘኔታ ‹‹ያለ ዛሬ እንደዚህ ሆኖ አያውቅም›› ሲል መለሰለት ‹‹ከዚህ በኋላ በወጀቡ ውስጥ ነው የምንጓዘው፤ ነገር ግን በቂ ነዳጅ ስለሌለን አደገኛ ነው››
‹‹እንዴት?›› ሲል ጠየቀ ቶም፡፡
‹‹ነዳጅ እያለቀ ነው››
ሉተር በድንጋጤ እንደተረበሸ ‹‹ታዲያ ነዳጅ እንደማይበቃ ከታወቀ
በጊዜ ወደ ኋላ እንመለሳለን ብለህ አልነበረም?››
ኤዲ ውስጡ ከሉተር በላይ ተሸብሯል፡፡ ነገር ግን ጠላቱ ቶም በመንቦቅቦቁ ረክቷል፡ ‹‹ወደ ኋላ መመለስ እንችል ነበር ነገር ግን የነዳጅ
ፍጆታ ስሌቱን አሳስቼ ስላሰላሁት የአይሮፕላኑ ሰራተኞች በቂ ነዳጅ ያለ
መስሏቸዋል፡፡ ከእናንተ ጋር ያለኝን ውጊያ ለማጠናቀቅ በቂ ምክንያት እንዳለኝ አስታወስክ?››
‹‹አንተ እብድ!›› አለ ሉተር ተስፋ ቆርጦ ‹ሁላችንንም ልትጨርሰን አስበሃል?››
‹‹እኔማ ሚስቴ በእናንተ እጅ መሆኗ ነው እንጂ እያንዳንድሽን ወሮበላ
ሁሉ አጠፋሽ ነበር››
‹‹ሁላችን ከሞትን ሚስትህን አታገኛትማ››
‹‹አውቃለሁ›› አለ ኤዲ ነገር ግን ሚስቱን በነዚያ አረመኔዎች እጅ ለአንድ ቀን እንኳን ሊተዋት አይፈልግም፡፡ ‹‹ምናልባተም አብጄ ሊሆን ይችላል›› አለ ኤዲ፡
ሉተር በጭንቀት እንደተወጠረ ‹‹ይሄ አይሮፕላን ባህር ላይ ያርፋል አይደል?››
‹‹የተገኘው ባህር ላይ ያርፋል ማለት አይደለም፡፡ አይሮፕላኑ ለማረፍ ፀጥ ያለ ባህር ይፈልጋል፤ ማዕበልና ወጀብ የበዛበት ባህር ላይ ልረፍ ካለ ብትንትኑ ነው የሚወጣው።
‹‹ወይ አምላኬ! እዚህ አይሮፕላን ውስጥ የተሳፈርኩት ምን አቅብጦኝ
አለ ቶም።
‹‹ሚስቴን ለማፈን የተነሳኸው ምን አቅብጦህ ነው?›› አለ ኤዲ ጥርሱን ነክሶ።
አይሮፕላኑ ድንገት ዘጭ ሲል ሉተር ወደ መጸዳጃ ክፍል ሮጠ፡፡
ኤዲ ተሳፋሪዎቹ ወዳሉበት ክፍል አመራ፡፡ ካርታ የሚጫወቱት ሰዎች
የመቀመጫ ቀበቶዎቻቸውን አስረዋል፡፡ አይሮፕላኑ ሲንዘፈዘፍና ሲወዛወዝ
ብርጭቆዎች ካርታዎችና ጠርሙሶች ምንጣፍ ላይ ይንከባለላሉ፡ኤዲ
ኮሪደሩ ላይ አማተረ፡፡ አሁን አይሮፕላኑ ፀጥ ብሎ መጓዝ ስለጀመረ
መኝታቸው ተመልሰው
ተሳፋሪዎች ተረጋግተዋል፡፡ አንዳንዶቹ ወደ መኝታቸው ተመልሰው በመቀመጫ ቀበቶዎች ተጠፍረዋል። በአይሮፕላኑ መወዛወዝ ከመውደቅ ለመዳን ከመታሰር ውጪ ሌላ ምርጫ እንደሌላቸው አውቀዋል፡፡ አንዳንዶቹ
ደግሞ መጋረጃቸውን ከፍተው ጋደም ብለዋል፡፡ አንዳንዶቹ ተሳፋሪዎች
ጉዞው ሰላማዊ ባይሆንም ፍርሃታቸውን ዋጥ አድርገው ይጫወታሉ።
አንዳንዶቹ ደግሞ ፍርሃቱ ሰቅዞ ይዟቸው መጫወቱንም ትተውታል
መጽሐፍት፣መነጽሮች፣ፒጃማዎች፣ አርቲፊሻል ጥርስ፣ሳንቲሞችና
አምባሮች ወለሉ ላይ ተበታትነው ይታያሉ፡፡ ኤዲ እሱ በፈጠረው ችግር
አይሮፕላኑ በወጀቡ ውስጥ ለመጓዝ በመገደዱ ምክንያት ያለ ቅጥ
በመወዛወዙ ተሳፋሪዎች መሰቃየታቸውን ሲያስበው በፀፀት ልቡ ተነካ፡፡ ይሄ
ሁሉ ሰውስ በእሱ ምክንያት ያልቅ ይሆን?›
ኤዲ ወደ መቀመጫው ሄደና ተቀመጠ፡፡ ከዚህ በኋላ ስለነዳጁ ፍጆታ
ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ ካሮል አንን ከነዚያ አረመኔዎች እጅ መንጭቆ
ለመውሰድ ያለው አማራጭ በዕቅዱ መሰረት የተባለው ቦታ ላይ አይሮፕላኑን በድንገት ማሳረፍ ብቻ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ኤዲ ዲኪን ራሱን ለመቆጣጠር ቢሞክርም ክዳኑ ተዘግቶ እንደሚንተከተክ ጀበና ሆኗል፡ በጭንቀት ሊፈነዳ ምንም አልቀረውም፡፡ ላቡ
አሁንም አሁንም ችፍ ይላል፡ ጨጓራው እየተቃጠለ በመሆኑ ሰውነቱ
እረፍት አጣ፡፡ ቀልቡን ሰብስቦ መስራት አልቻለም፡፡
ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ የእሱ ፈረቃ ያበቃል ወደ መውጫው ሰዓት ላይ የሀሰት የነዳጅ ፍላጎት መጠን አስልቶ በሰንጠረዡ ላይ አሰፈረ።
ካፒቴኑ ጉዞውን
ለማጠናቀቅ የሚያስችል በቂ ነዳጅ ያለው
ለማስመሰልና ወደ ኋላ እመለሳለሁ እንዳይል የአይሮፕላኑን የነዳጅ ፍጆታ
ፍላጎት መጠን አሳንሶ አስልቶ ነበር፡፡ የእሱ ተተኪ የሆነው ሚኪ ፊን ሲመጣ ልዩነቱን እንዳያውቅ የፍጆታ መጠኑን ከፍ አድርጎ በማስላት አካካሰው፡፡ የነዳጅ ፍጆታ መጠን በወጣ ገባነት መለዋወጡን ሚኪ ሲያይ ምን ተፈጠረ ብሎ መጠየቁ አይቀርም፡፡ ኤዲም ይህ የሆነው በወጀቡ ምክንያት ነው ሊለው ተዘጋጅቷል፡፡ የሆነ ሆኖ አሁን ሚኪ ምን እንደሚል ሳይሆን ያስጨነቀው፣ አዕምሮውን የውጥር የያዘው አይሮፕላኑ ኒውፋውንድ ላንድ (ካናዳ) ሳይደርስ ነዳጅ ይጨርስ ይሆን የሚለው ሃሳብ ነው፡፡
የበረራ ህጉ መያዝ ያለበትን መጠባበቂያ የነዳጅ መጠን ቢያስቀምጥም
አይሮፕላኑ የራሱ የሆነ ዝቅተኛ የነዳጅ ፍጆታ መጠን ደንብ የለውም:
አይሮፕላኑም ከአቅም በላይ ለሆነ ችግር የመጠባበቂያ ነዳጅ የለውም::በነዳጅ ችግር ምክንያት አንድ ችግር ቢከሰት አይሮፕላኑ ያለ ጥርጥር ማዕበል በበዛበት አትላንቲክ ውቂያኖስ ውስጥ መውደቁ አይቀርም፡፡ ከወደቀ
ደግሞ በትንሽ ደቂቃ ውስጥ ስለሚሰምጥ ለወሬ ነጋሪ እንኳን የሚተርፍ
የለም፡፡
ሚኪ እንደወትሮው ነቃ ብሎና ለስራ ተነሳስቶ ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት
ሲል ደረሰ፡፡ ‹‹ያለን ነዳጅ አነስተኛ መሆኑን ለካፒቴኑ ነግሬያለሁ›› አለው
ኤዲ፡፡
ሚኪም ያለው ነገር ብዙም ስሜት እንዳልሰጠው ሁሉ ራሱን በማነቃነቅ ብቻ መረዳቱን ገለፀለትና ባትሪውን አነሳ፡፡ የመጀመሪያ ስራው የአይሮፕላኑ አራት ሞተሮች በዓይን መቃኘት ነው፡፡
ኤዲ ሚኪን ባለበት ቦታ ትቶ ወደ ተሳፋሪዎች ክፍል አመራ፡ ረዳት.ካፒቴኑ ጆኒ ዶት ናቪጌተሩ ጃክ አሽፎርድና ሬዲዮ ኦፕሬተሩ ቤን ቶምስን ተከትለውታል፡፡ ጃክ ለራሱ ሳንድዊች ሊያዘጋጅ ወደ ኩሽና ሄደ፡፡ ኤዲ ምግብ መብላት አይደለም ምግብ ሲያይ ሊያስታውከው ስለሚደርስ አንድ ሲኒ ቡና ብቻ ጠጣ
ስራ በሌለው ሰዓት ባለቤቱ ካሮል አን በነዚያ አፋኞች መዳፍ ስር መሆኗ ብቻ ነው አዕምሮው ውስጥ የሚመጣው፡፡
አሁን በአሜሪካ ሜይን ስቴት ውስጥ ሰዓቱ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በመሆኑ ጨለማ ነው፡፡ ይሄን ጊዜ ካሮል አን ከመንገላታት ብዛት ዝላና ልቧ
ተሰብሮ ቁጭ ብላ ይሆናል፡፡ ነፍሰ ጡር ከሆነች ወዲህ በጊዜ ነው
የምትተኛው፡ ታዲያ እንድትተኛ ይፈቅዱላት ይሆን? መተኛት ቀርቶ
ጎኗን የምታሳርፍበት ቦታ ቢሰጧት ጥሩ ነበር፡፡
ምሽቱ እየገፋ ሲሄድ ሚስቱን ያገቷት ወሮበሎች ሌላ ክፉ ነገር ያውጠነጥኑ ይሆን? ሲል መጨነቅ ጀመረ፡፡
ወጀቡ እንደገና ተነሳ፡፡
አይሮፕላኑ መናጡ ባሰበት፡ በማዕበል ላይ የሚጓዝ መርከብ መስሏል፡ ግዙፍ አይሮፕላን አንዴ ከፍ እያለ አንዴ ዝቅ እያለ በንፋስ ወዲህ ወዲያ የተንገላታ ይጓዛል። ተሳፋሪዎቹ ስጋት ገብቷቸው ከእንቅልፋቸው ተነሱ አስተናጋጁንም ይጣሩ ጀመር፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ሆዳቸው ታውኮ ወደ
መጸዳጃ ክፍል ይሮጣሉ አስተናጋጆቹም ወደ ተሳፋሪዎቹ ተራወጡ፡
ኤዲ ቡና ለመጠጣት ሲሄድ ቶም ሉተር ፊቱ መጥቶ ድቅን አለ፡፡ሉተር በአይሮፕላኑ መናወጥ ደንግጦ ፊቱ አመድ መስሏል፡ ሰውነቱ በላብ
ርሷል፡ ኤዲም ጅንን ብሎ ያየዋል፡፡ ቶምን ጉሮሮውን ፈጥርቆ ሊይዘው ትንሽ ነበር የቀረው፤ ነገር ግን ንዴቱን ውጦ ዝም አለ፡፥
‹‹ይሄ ግን የተለመደ ነው?›› ሲል ጠየቀ ቶም በፍርሃት፡
ኤዲ ያለ ምንም ሀዘኔታ ‹‹ያለ ዛሬ እንደዚህ ሆኖ አያውቅም›› ሲል መለሰለት ‹‹ከዚህ በኋላ በወጀቡ ውስጥ ነው የምንጓዘው፤ ነገር ግን በቂ ነዳጅ ስለሌለን አደገኛ ነው››
‹‹እንዴት?›› ሲል ጠየቀ ቶም፡፡
‹‹ነዳጅ እያለቀ ነው››
ሉተር በድንጋጤ እንደተረበሸ ‹‹ታዲያ ነዳጅ እንደማይበቃ ከታወቀ
በጊዜ ወደ ኋላ እንመለሳለን ብለህ አልነበረም?››
ኤዲ ውስጡ ከሉተር በላይ ተሸብሯል፡፡ ነገር ግን ጠላቱ ቶም በመንቦቅቦቁ ረክቷል፡ ‹‹ወደ ኋላ መመለስ እንችል ነበር ነገር ግን የነዳጅ
ፍጆታ ስሌቱን አሳስቼ ስላሰላሁት የአይሮፕላኑ ሰራተኞች በቂ ነዳጅ ያለ
መስሏቸዋል፡፡ ከእናንተ ጋር ያለኝን ውጊያ ለማጠናቀቅ በቂ ምክንያት እንዳለኝ አስታወስክ?››
‹‹አንተ እብድ!›› አለ ሉተር ተስፋ ቆርጦ ‹ሁላችንንም ልትጨርሰን አስበሃል?››
‹‹እኔማ ሚስቴ በእናንተ እጅ መሆኗ ነው እንጂ እያንዳንድሽን ወሮበላ
ሁሉ አጠፋሽ ነበር››
‹‹ሁላችን ከሞትን ሚስትህን አታገኛትማ››
‹‹አውቃለሁ›› አለ ኤዲ ነገር ግን ሚስቱን በነዚያ አረመኔዎች እጅ ለአንድ ቀን እንኳን ሊተዋት አይፈልግም፡፡ ‹‹ምናልባተም አብጄ ሊሆን ይችላል›› አለ ኤዲ፡
ሉተር በጭንቀት እንደተወጠረ ‹‹ይሄ አይሮፕላን ባህር ላይ ያርፋል አይደል?››
‹‹የተገኘው ባህር ላይ ያርፋል ማለት አይደለም፡፡ አይሮፕላኑ ለማረፍ ፀጥ ያለ ባህር ይፈልጋል፤ ማዕበልና ወጀብ የበዛበት ባህር ላይ ልረፍ ካለ ብትንትኑ ነው የሚወጣው።
‹‹ወይ አምላኬ! እዚህ አይሮፕላን ውስጥ የተሳፈርኩት ምን አቅብጦኝ
አለ ቶም።
‹‹ሚስቴን ለማፈን የተነሳኸው ምን አቅብጦህ ነው?›› አለ ኤዲ ጥርሱን ነክሶ።
አይሮፕላኑ ድንገት ዘጭ ሲል ሉተር ወደ መጸዳጃ ክፍል ሮጠ፡፡
ኤዲ ተሳፋሪዎቹ ወዳሉበት ክፍል አመራ፡፡ ካርታ የሚጫወቱት ሰዎች
የመቀመጫ ቀበቶዎቻቸውን አስረዋል፡፡ አይሮፕላኑ ሲንዘፈዘፍና ሲወዛወዝ
ብርጭቆዎች ካርታዎችና ጠርሙሶች ምንጣፍ ላይ ይንከባለላሉ፡ኤዲ
ኮሪደሩ ላይ አማተረ፡፡ አሁን አይሮፕላኑ ፀጥ ብሎ መጓዝ ስለጀመረ
መኝታቸው ተመልሰው
ተሳፋሪዎች ተረጋግተዋል፡፡ አንዳንዶቹ ወደ መኝታቸው ተመልሰው በመቀመጫ ቀበቶዎች ተጠፍረዋል። በአይሮፕላኑ መወዛወዝ ከመውደቅ ለመዳን ከመታሰር ውጪ ሌላ ምርጫ እንደሌላቸው አውቀዋል፡፡ አንዳንዶቹ
ደግሞ መጋረጃቸውን ከፍተው ጋደም ብለዋል፡፡ አንዳንዶቹ ተሳፋሪዎች
ጉዞው ሰላማዊ ባይሆንም ፍርሃታቸውን ዋጥ አድርገው ይጫወታሉ።
አንዳንዶቹ ደግሞ ፍርሃቱ ሰቅዞ ይዟቸው መጫወቱንም ትተውታል
መጽሐፍት፣መነጽሮች፣ፒጃማዎች፣ አርቲፊሻል ጥርስ፣ሳንቲሞችና
አምባሮች ወለሉ ላይ ተበታትነው ይታያሉ፡፡ ኤዲ እሱ በፈጠረው ችግር
አይሮፕላኑ በወጀቡ ውስጥ ለመጓዝ በመገደዱ ምክንያት ያለ ቅጥ
በመወዛወዙ ተሳፋሪዎች መሰቃየታቸውን ሲያስበው በፀፀት ልቡ ተነካ፡፡ ይሄ
ሁሉ ሰውስ በእሱ ምክንያት ያልቅ ይሆን?›
ኤዲ ወደ መቀመጫው ሄደና ተቀመጠ፡፡ ከዚህ በኋላ ስለነዳጁ ፍጆታ
ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ ካሮል አንን ከነዚያ አረመኔዎች እጅ መንጭቆ
ለመውሰድ ያለው አማራጭ በዕቅዱ መሰረት የተባለው ቦታ ላይ አይሮፕላኑን በድንገት ማሳረፍ ብቻ ነው፡፡
👍17
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“አፈርሁኝ በራሴ ከሎ!
“ሃፍረት ልብሳችን ሆኗል፡ በተለይ ከዚች ሃገር ወጣ ብለህ ስትመለስ የት ነን? ማን ይዞ አስቀረን?... ሺ ጥያቄ በህሊናሀ ይደረደራል። መልሱን ግን አታገኘውም! የሚመልስልህም የለም::
“መጽሐፍ ስታነብ ያለፉትን የኪነ ጥበብ ስራዎች ስታይ
በታላላቆቻችንና በኛ መካከል ያለው ግሉህ ልዩነት ያፈጥብሃል
ጠልፎ እሚጥል ! ጉቶ ይመስል እንቅፋት ሆኖ ለመስራት የሚፍጨረጨሩትን የሚያደናቅፍ ምክንያት ይኖራል! ደግሞ አለ!
ነበረም።
“ይህ ግን በእንቅልፍ ለመደበቅ በቂ ምክንያት አይደለም ችግር ሲበዛ መፍትሄውም ከውስጡ ይፈለፈላል። ለመሻሻል ምንጩ ችግር እርካታ ማጣት ነው:
“እኛ ግን ብዙ አጥተን ብዙ ነገር ካላቸው በላይ ቆመን
እናናውዛለን። ብቸኛ ሆነን አጠገባችን ያሉትን እናኮርፋለን እንኮንናለን
ከመሃከላችን ለመውጣትና እኛኑ ለመሳብ
የሚንቀሳቀሰውን ሞራል እየስጠን ከማደፋፈር ይልቅ ተጋግዘን በጠረባ እንዘርረዋለን። የኛ ደስታ የሚታየው በወደቀው ስንስቅ ነው ሌሎቹ ደግሞ በእኛ በወደቅነው ይሳለቁብናል።
“ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን ከመከበር ራሳችንን
አራቅን ያለንን አናውቅም! ሌላው ቀርቶ ባለንም አኮራም፡ ከዚያ ይልቅ በተውሶ አልባሳትና ቅራቅንቦ የማስመሰል ተውኔት በባለቤቶቹና በእኛው ህዝብ ፊት እንሰራለን፡ ሁለቱም ግን ረክተው አያጨበጭቡልንም! ከሁለት ያጣ ጎመን' ነን…”
ሶራ በከሎ ሃሳብ መመሰጡና መስማማቱ በሚተናነቀው እልህ ያስታውቃል።
“ሳይጠባበቁ ለስራ መነሳት አስፈላጊ ነው" ብሎ ሶራ ትንሽ አሰብ አደረገና፡-
“ይህችን ሃገር ግን አቅጣጫዋ ወዴት ይሆን የሚለውን ለመመለስ ይከብዳል፤ ወደ ተፈጥሯዊ ሕይወት ወይንስ ወደ ዘመናዊ ኑሮን ሔ? ይህ ሃሳብ በህዝቡ ሲመለስ ህዝቡ ያሰበው ጋ ለመድረስ
መጣጣር ይጀምራል፡ አሁን ግን ያለው ነገር ዝብርቅርቁ የወጣ ነው እስኪ አስበው ጉዟችን እውነት ወዴት ነው? አለና ሃሳቡን ገቶ ከሎን አየው: ሁለቱም ጆሮ ላይ የሚያላዝን ውሻ ጩኸት
የመሰለ ኦምቧረቀ።
“ግን አንድ እውነት አለ፡ አንድ ወቅት የቀደምናቸው
አገሮች አሁን ጥለውን ተፈትልከዋል። እነሱ ዘንድ ለመድረስ ቀጥሎም ለማለፍ በእልህ የታገዘ ጥረት ያስፈልጋል! ከኋላችን
ተነስተው አሁን ከፊት የሚገኙት ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑን ይገባል::
መላና ዘዴ ሳንቀይስ፤ የምንነሳበትንና የምንደርስበትን... ሳናውቅ ግን በለመድናት ጠባብ ጎዳና እንጓዝ ካልን አንዱ መሄጃችን ላይ ገብቶ
ሲሰነቀር ሌላው እንደተለመደው ቆሞ ይቀራል። ለዚህ ሁሉ ግን
ከየት እንጀምር?'' አለ ሶራ ጥያቄ እያቀረበ መልሱን ራሱ ለመመለስ።
“ከራሳችን ከራሳችን መጀመር አለብን" በስሜት ያቀረበው ሃሳብ እንደ ጦር ጎኑን ወጋው። ባዶ ምኞት ወይንስ በተግባር የሚውል ህልም... ፍቅሯ ልቡን እንደ ክትፎ የበላበት ኮንችትስ?
ከሎና ሶራ አንዱ ሌላውን ይበልጥ ለማወቅ፤ ተረዳድተው የአገራቸው አለኝታ ለመሆን ህሊናቸው ቋምጧል: የውጪ ዓለም
ልምዳቸው በራስ መተማመናቸውን ብትንትኑን ቢያወጣቸውም ማንነታቸውን ግን እንደ መስታዋት ቁልጭ አድርጎ አሳይቷቸዋል።
በዚህ የአድቬንቼር ዘመን በትርኪ ምርኪው የግደለሽነት ሕይወት መኖር እንደ አበቅ አንጓሉ አንጓሉ የሐፍረት ቆሻሻ ላይ
እንደሚጥል ተረድተዋል ከሌላው መማር እንጂ እንደ ተውሳክ ጥገኛ መሆን አይንን ጨፍኖ መለመን... በቁም ከመሞት በሞራል
ከመላሸቅ በቀር የሚያመጣው ህሊናዊ ጥጋብ አለመኖሩን ከሕይወት ገጠመኞቻቸው አንፃር አንስተው ብዙ ጊዜ ተጨዋውተዋል::
በህዳሩ የመኸር ወቅት ጨረቃ እንደ ቡሄ ዳቦ ክብ ሆና ገና የብርሃን ወጋገኗን በኒያንጋቶም ተራሮች ወደ ኩዩጉ መንደር ወደ
ኩችሩ ስትፈነጥቅ ከሎና ሶራ እንደተለመደው ሃሳብ ሲለዋወጡ እንደ ቆዩ በመካከላቸው ዝምታ ሰፈነና በእዝነ ሊናቸው ሰማዩ ላይ ጎላ ብሎ የተፃፈ ነገር ተመለከቱ ያን ፅሑፍ ሁለቱም ቀና ብለው አዩት።
“የህይወት ጀልባ ከማዕበል ጋር እየታገለች በውቅያኖሶች ጉያ
አካሏን ነክራ ትንሳፈፋለች ሞት ችግር መከራ ... ያደፍቋታል፤ ደስታ እርካታ ፍቅር. እንደ እንዝርት እያሾሩ ይፈትሏታል እና ጀልባዋ በሁለቱ እጣ ፈንታ ሚዛኗን ጠብቃı የተኙትን የሚስሩት
እየረጋገጧቸው ትሰሩለች:
“በእርገጥ የጎደለው ይተካል ያጣው ያገኛል! ያፈቀረ ይጠላል! የተለጣለ ያነሳል፤የሄደ ይመጣል... በተቃራኒዎች የተወጠረችው ጀልባ የሚፈራረቁባትን ችላ ትጓዛለች።
“አቅጣጫዋ መነሻ መድረሻዋ አይታወቅም:: ጀልባዋ አልቆላታል ትባል እንጂ ከጉዞዋ ከቶ ተገታ አታውቅም: አንድ ቀን
ግን ሥቃይና ሰቆቃ፤ እብሪትና ግፍ የበዛባት ጀልባ ብልሽት
ይገጥማት ይሆናል ያኔ ተሳፋሪዎችዋን ይዛ ትዘቅጣለች ቁልቁል!
“እሪታ ሰማዩን ያቀልጠዋል የቀስተ ዳመና ቀለሞች በሺ
ተባዝተው ሰማዩን ያስውቡታል ከዋክብት ከነበሩበት በታች ዝቅ
ብለው ብርሃናቸውን ያንተገትጋሉ ገነትና መንግሥተ ሰማያት
ይጣመራሉ።
“ሟቹ ያን ውብ ሰማይ ርቆት ሲሄድ እማይጠገብ
ይሆንበታል! ጀልባዋ ስትዘቅጥ ተስፋ የቆረጠ ያለቅሳል... ሰሚና
ጯሂ እንዲሆ በአንድ ጀልባ ሆነው ዋይ ዋይ' ሲሉ ስቃይ እንደ ቅርጫት ላያቸው ላይ ሲከደንባቸው ይወርዳል።
“በዚያ ሰዓት ቅድስት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ሰማይ ትዘረጋለች አምላኳም ድምጿን ሰምቶ ህዝቧን ስለ ስንፍናው አምርሮ ይገስፀዋል።
“እጆቻችሁ ስለምን ሽባ ሆኑ! ስለምንስ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅን መረጣችሁ... ሆድ ብቻ. ጥቅምን ማነፍነፍ ብቻ... ብሎ አዝኖ ውቅያኖሱን ሜዳ ያደርገዋል ድህነትም በምድር ይወርዳል….ልብ ያለው ልብ ይበል" ይላል ሶራና ከሎ አይናቸውን ጨፍነው ያነበቡት።
በጥቁር የሰማይ ሰሌዳ የተፃፈውን ታምር 'ሁለቱም
እየደጋገሙ አነበቡት:
እንግዳው አጋጣሚ
አስገረማቸው አስፈራቸው ... ያ አጉራሽ የለመደው ህሊናቸው ግን ትርጉሙን በጊዜው ሊያቀርብላቸው አልቻለም።
“የምን ጽሑፍ ነው?... ማንስ ፃፈው?...በየግል የፍች "ቀመሩን ለማግኘት ዳንኪራ ረጋጭ ህሊናቸውን አስጨፈሩት። አንዱ
ለሌላው ያየውን ሚስጥር ግን አላወጣም።
ችግርን ለመናድ ማነስ የሚያመጣውን የአዕምሮ ሰንካላነት ለማስቀረት በራስ የመተማመንን ተፈጥሯዊ ፀጋ ጠብቆ ልጅ የልጅ
ልጆችን ከሃፍረት ለማዳን ሆዳምነትን አስወግዶ በእጅና አዕምሮ መጠቀም... ጀልባዋ ሳትሰጥም ደካማ ጎንን ማስተካከል እንደሚገባ
ዘግይተውም ቢሆን የተረዱ ይመስላል።
በዚያች ሰዓት ከሎና ሶራ ተያዩ! ኤርቦሬና ሐመሩ
ሁለቱ አፍሪካውያን ሊግባቡ
ሞከሩ! ሃይላቸውን ለማስተባበር ተቃቀፉደ
ፍቅራቸው ስህተታቸው ቁጭታቸው... ያስፈነደቃት ጨረቃም አላማቸውን ለማጠንhር ብርሃኗን እያሰፋች ፍጥነቷን በመጨር ጥቁሩን ሰማይ እየገለጠች ወደ እነሱ ገሠገሠች።
ከዚያ ያ ኩሩው ድፍርሱ ሚሊዮን ነፍሳትን በውስጡ
አጭቆ ቁልቁል ይሁን ሽቅብ መፍሰሱ ሳይታወቅ በፀጥታ የሚጓዘው ኦሞ ወንዝ በቁጭት አፍ አውጥቶ ሲናገር! እንደ ውሻ ሲጮህ ተሰማ።
"ኢትዮጵያ ፈላስፎቿን ተመራማሪዎቿን የንብ ተምሳሌት ታታሪ ምሁሮቿን, ማቀፍ እርስ በርሳቸው በጡንቻ ሳይሆን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“አፈርሁኝ በራሴ ከሎ!
“ሃፍረት ልብሳችን ሆኗል፡ በተለይ ከዚች ሃገር ወጣ ብለህ ስትመለስ የት ነን? ማን ይዞ አስቀረን?... ሺ ጥያቄ በህሊናሀ ይደረደራል። መልሱን ግን አታገኘውም! የሚመልስልህም የለም::
“መጽሐፍ ስታነብ ያለፉትን የኪነ ጥበብ ስራዎች ስታይ
በታላላቆቻችንና በኛ መካከል ያለው ግሉህ ልዩነት ያፈጥብሃል
ጠልፎ እሚጥል ! ጉቶ ይመስል እንቅፋት ሆኖ ለመስራት የሚፍጨረጨሩትን የሚያደናቅፍ ምክንያት ይኖራል! ደግሞ አለ!
ነበረም።
“ይህ ግን በእንቅልፍ ለመደበቅ በቂ ምክንያት አይደለም ችግር ሲበዛ መፍትሄውም ከውስጡ ይፈለፈላል። ለመሻሻል ምንጩ ችግር እርካታ ማጣት ነው:
“እኛ ግን ብዙ አጥተን ብዙ ነገር ካላቸው በላይ ቆመን
እናናውዛለን። ብቸኛ ሆነን አጠገባችን ያሉትን እናኮርፋለን እንኮንናለን
ከመሃከላችን ለመውጣትና እኛኑ ለመሳብ
የሚንቀሳቀሰውን ሞራል እየስጠን ከማደፋፈር ይልቅ ተጋግዘን በጠረባ እንዘርረዋለን። የኛ ደስታ የሚታየው በወደቀው ስንስቅ ነው ሌሎቹ ደግሞ በእኛ በወደቅነው ይሳለቁብናል።
“ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን ከመከበር ራሳችንን
አራቅን ያለንን አናውቅም! ሌላው ቀርቶ ባለንም አኮራም፡ ከዚያ ይልቅ በተውሶ አልባሳትና ቅራቅንቦ የማስመሰል ተውኔት በባለቤቶቹና በእኛው ህዝብ ፊት እንሰራለን፡ ሁለቱም ግን ረክተው አያጨበጭቡልንም! ከሁለት ያጣ ጎመን' ነን…”
ሶራ በከሎ ሃሳብ መመሰጡና መስማማቱ በሚተናነቀው እልህ ያስታውቃል።
“ሳይጠባበቁ ለስራ መነሳት አስፈላጊ ነው" ብሎ ሶራ ትንሽ አሰብ አደረገና፡-
“ይህችን ሃገር ግን አቅጣጫዋ ወዴት ይሆን የሚለውን ለመመለስ ይከብዳል፤ ወደ ተፈጥሯዊ ሕይወት ወይንስ ወደ ዘመናዊ ኑሮን ሔ? ይህ ሃሳብ በህዝቡ ሲመለስ ህዝቡ ያሰበው ጋ ለመድረስ
መጣጣር ይጀምራል፡ አሁን ግን ያለው ነገር ዝብርቅርቁ የወጣ ነው እስኪ አስበው ጉዟችን እውነት ወዴት ነው? አለና ሃሳቡን ገቶ ከሎን አየው: ሁለቱም ጆሮ ላይ የሚያላዝን ውሻ ጩኸት
የመሰለ ኦምቧረቀ።
“ግን አንድ እውነት አለ፡ አንድ ወቅት የቀደምናቸው
አገሮች አሁን ጥለውን ተፈትልከዋል። እነሱ ዘንድ ለመድረስ ቀጥሎም ለማለፍ በእልህ የታገዘ ጥረት ያስፈልጋል! ከኋላችን
ተነስተው አሁን ከፊት የሚገኙት ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑን ይገባል::
መላና ዘዴ ሳንቀይስ፤ የምንነሳበትንና የምንደርስበትን... ሳናውቅ ግን በለመድናት ጠባብ ጎዳና እንጓዝ ካልን አንዱ መሄጃችን ላይ ገብቶ
ሲሰነቀር ሌላው እንደተለመደው ቆሞ ይቀራል። ለዚህ ሁሉ ግን
ከየት እንጀምር?'' አለ ሶራ ጥያቄ እያቀረበ መልሱን ራሱ ለመመለስ።
“ከራሳችን ከራሳችን መጀመር አለብን" በስሜት ያቀረበው ሃሳብ እንደ ጦር ጎኑን ወጋው። ባዶ ምኞት ወይንስ በተግባር የሚውል ህልም... ፍቅሯ ልቡን እንደ ክትፎ የበላበት ኮንችትስ?
ከሎና ሶራ አንዱ ሌላውን ይበልጥ ለማወቅ፤ ተረዳድተው የአገራቸው አለኝታ ለመሆን ህሊናቸው ቋምጧል: የውጪ ዓለም
ልምዳቸው በራስ መተማመናቸውን ብትንትኑን ቢያወጣቸውም ማንነታቸውን ግን እንደ መስታዋት ቁልጭ አድርጎ አሳይቷቸዋል።
በዚህ የአድቬንቼር ዘመን በትርኪ ምርኪው የግደለሽነት ሕይወት መኖር እንደ አበቅ አንጓሉ አንጓሉ የሐፍረት ቆሻሻ ላይ
እንደሚጥል ተረድተዋል ከሌላው መማር እንጂ እንደ ተውሳክ ጥገኛ መሆን አይንን ጨፍኖ መለመን... በቁም ከመሞት በሞራል
ከመላሸቅ በቀር የሚያመጣው ህሊናዊ ጥጋብ አለመኖሩን ከሕይወት ገጠመኞቻቸው አንፃር አንስተው ብዙ ጊዜ ተጨዋውተዋል::
በህዳሩ የመኸር ወቅት ጨረቃ እንደ ቡሄ ዳቦ ክብ ሆና ገና የብርሃን ወጋገኗን በኒያንጋቶም ተራሮች ወደ ኩዩጉ መንደር ወደ
ኩችሩ ስትፈነጥቅ ከሎና ሶራ እንደተለመደው ሃሳብ ሲለዋወጡ እንደ ቆዩ በመካከላቸው ዝምታ ሰፈነና በእዝነ ሊናቸው ሰማዩ ላይ ጎላ ብሎ የተፃፈ ነገር ተመለከቱ ያን ፅሑፍ ሁለቱም ቀና ብለው አዩት።
“የህይወት ጀልባ ከማዕበል ጋር እየታገለች በውቅያኖሶች ጉያ
አካሏን ነክራ ትንሳፈፋለች ሞት ችግር መከራ ... ያደፍቋታል፤ ደስታ እርካታ ፍቅር. እንደ እንዝርት እያሾሩ ይፈትሏታል እና ጀልባዋ በሁለቱ እጣ ፈንታ ሚዛኗን ጠብቃı የተኙትን የሚስሩት
እየረጋገጧቸው ትሰሩለች:
“በእርገጥ የጎደለው ይተካል ያጣው ያገኛል! ያፈቀረ ይጠላል! የተለጣለ ያነሳል፤የሄደ ይመጣል... በተቃራኒዎች የተወጠረችው ጀልባ የሚፈራረቁባትን ችላ ትጓዛለች።
“አቅጣጫዋ መነሻ መድረሻዋ አይታወቅም:: ጀልባዋ አልቆላታል ትባል እንጂ ከጉዞዋ ከቶ ተገታ አታውቅም: አንድ ቀን
ግን ሥቃይና ሰቆቃ፤ እብሪትና ግፍ የበዛባት ጀልባ ብልሽት
ይገጥማት ይሆናል ያኔ ተሳፋሪዎችዋን ይዛ ትዘቅጣለች ቁልቁል!
“እሪታ ሰማዩን ያቀልጠዋል የቀስተ ዳመና ቀለሞች በሺ
ተባዝተው ሰማዩን ያስውቡታል ከዋክብት ከነበሩበት በታች ዝቅ
ብለው ብርሃናቸውን ያንተገትጋሉ ገነትና መንግሥተ ሰማያት
ይጣመራሉ።
“ሟቹ ያን ውብ ሰማይ ርቆት ሲሄድ እማይጠገብ
ይሆንበታል! ጀልባዋ ስትዘቅጥ ተስፋ የቆረጠ ያለቅሳል... ሰሚና
ጯሂ እንዲሆ በአንድ ጀልባ ሆነው ዋይ ዋይ' ሲሉ ስቃይ እንደ ቅርጫት ላያቸው ላይ ሲከደንባቸው ይወርዳል።
“በዚያ ሰዓት ቅድስት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ሰማይ ትዘረጋለች አምላኳም ድምጿን ሰምቶ ህዝቧን ስለ ስንፍናው አምርሮ ይገስፀዋል።
“እጆቻችሁ ስለምን ሽባ ሆኑ! ስለምንስ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅን መረጣችሁ... ሆድ ብቻ. ጥቅምን ማነፍነፍ ብቻ... ብሎ አዝኖ ውቅያኖሱን ሜዳ ያደርገዋል ድህነትም በምድር ይወርዳል….ልብ ያለው ልብ ይበል" ይላል ሶራና ከሎ አይናቸውን ጨፍነው ያነበቡት።
በጥቁር የሰማይ ሰሌዳ የተፃፈውን ታምር 'ሁለቱም
እየደጋገሙ አነበቡት:
እንግዳው አጋጣሚ
አስገረማቸው አስፈራቸው ... ያ አጉራሽ የለመደው ህሊናቸው ግን ትርጉሙን በጊዜው ሊያቀርብላቸው አልቻለም።
“የምን ጽሑፍ ነው?... ማንስ ፃፈው?...በየግል የፍች "ቀመሩን ለማግኘት ዳንኪራ ረጋጭ ህሊናቸውን አስጨፈሩት። አንዱ
ለሌላው ያየውን ሚስጥር ግን አላወጣም።
ችግርን ለመናድ ማነስ የሚያመጣውን የአዕምሮ ሰንካላነት ለማስቀረት በራስ የመተማመንን ተፈጥሯዊ ፀጋ ጠብቆ ልጅ የልጅ
ልጆችን ከሃፍረት ለማዳን ሆዳምነትን አስወግዶ በእጅና አዕምሮ መጠቀም... ጀልባዋ ሳትሰጥም ደካማ ጎንን ማስተካከል እንደሚገባ
ዘግይተውም ቢሆን የተረዱ ይመስላል።
በዚያች ሰዓት ከሎና ሶራ ተያዩ! ኤርቦሬና ሐመሩ
ሁለቱ አፍሪካውያን ሊግባቡ
ሞከሩ! ሃይላቸውን ለማስተባበር ተቃቀፉደ
ፍቅራቸው ስህተታቸው ቁጭታቸው... ያስፈነደቃት ጨረቃም አላማቸውን ለማጠንhር ብርሃኗን እያሰፋች ፍጥነቷን በመጨር ጥቁሩን ሰማይ እየገለጠች ወደ እነሱ ገሠገሠች።
ከዚያ ያ ኩሩው ድፍርሱ ሚሊዮን ነፍሳትን በውስጡ
አጭቆ ቁልቁል ይሁን ሽቅብ መፍሰሱ ሳይታወቅ በፀጥታ የሚጓዘው ኦሞ ወንዝ በቁጭት አፍ አውጥቶ ሲናገር! እንደ ውሻ ሲጮህ ተሰማ።
"ኢትዮጵያ ፈላስፎቿን ተመራማሪዎቿን የንብ ተምሳሌት ታታሪ ምሁሮቿን, ማቀፍ እርስ በርሳቸው በጡንቻ ሳይሆን
👍18👏1🤔1
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
በቀጠሯችን መሰረት ወደቃል ቤት እየሄደች ነው።ይህ ቀጠሮ ለእሷ ልክ እንደከዚ ቀደሞቹ ቀጠሮዎች አይነት አይደለም።ቀጠሮውን ሳታሲዘው እንኳን "ለብቻህ ለረጂም ሰዓት ነው የምፈልግህ..በምንም አይነት የማይሰረዝ የሞት ቀጠሮ ነው"ነበር ያለችው።ልክ ስድስት ሰዓት እሱ ቤት ለመገናኘት ነው የተቀጣጠሩት። ሁለት ሰዓት ከቤት ወጣች፤ የውበት ሳሎን ደንበኞቾ ጋር ሄደች ...ከጥፍሯ አንስቶ ቅንድቧን ፀጉሯን እስክታስተካክልላት አራት ተኩል ሆነ...እቤት ሄዳ በሀገሪቱ አለ በተባለች ዲዛይነር በልዩ ሁኔታ ያሰፋችውን የሀገር በሀል ቀሚስ ለብሳ እሱን ደስ ያሰኘዋል ብላ ባሰችው አለባበስ ዘንጣ መኪናዋን እሱ የሚኖርበት ግቢ አስገብታ ስታቆም ሰዓቱ 6.03 ይል ነበር።የመኪናዋን ሞተር ከጠፋችና ለእለቱ ልዪ ዝግጅት ማድመቂያ ይሆን ዘንድ ይዛ የመጣችውን ቶርታ ኬክ፤ውስኪ፤ሻማዎች እና ቸኮሌቶችን ከእነ ዘንቢሉ እየተንገዳገደችም ቢሆን ይዛ ወረደችና ወደ ቃል ቤት ልትታጠፍ ስትል አሮጊቷ የቤት አከራይ ከእቤታቸው ሲወጡ ተገጣጠሙ ።
"ውይ በጌታ መጣሽ?"አሉ ከሞት የተነሳ ዘመዳቸውን ድንገት እንዳዩ አይነት ደንግጠው። የአሮጊቷ መደንገጥ ብቻ ሳይሆን እንባቸውም እየረገፈ ነው ።
" ማዘር ምን ሆኑ?"
‹‹አረ ምንም አልሆንኩ..ምነው ጠየቅሺኝ?"
"አይ እያለቀሱ ነው ብዬ ነዋ"
"እ አይ ልጄ ጭስ ነገር ነበር ..እቤት ያው ያሮጊት ነገር ታውቂ የለ"
"በሉ እሺ"ብላ መንገዷን ስትቀጥል
"ቆይ ልጄ ቁልፍ ልስጥሸ"አሏትና አስቆሟት፡፡
ውስጧን ክፍት አለው"ምነው ቃል የለም እንዴ?››ለስለስ ባለ ድምፀት ጠየቀቻቸው ።
"ቃል ነው ያልሽው ?"አሉና ወደውስጥ መግባቱን እረስተው ፍዝዝ ብለው ቆሙ፡
"እንዴ እማማ ..ችግር አለ እንዴ?"
"አረ የለም..ማለቴ ቃል ወጣ ብሎ ነው አልቆይም ብሎል"ብለዋት ወደ ውስጥ ገቡ ።
"ቃል ደግሞ በዚህ ቀን?ለዛውም እንዲህ አስጠንቅቄህ"ቃል ስሯ ሆኖ ባይሰማትም ተነጫነጨችበት ።
አሮጊቷ አምጥተው ቁልፍን ሰጧት... ነገረ ስራቸው አላማራትም‹..አይናቸውን ከዓይኔ ለምንድነው የሚያሸሹት?›ቁልፉን ተቀብላ እያልጎመጎመች ወደጓሮ ዞረችና የቃልን ቤት ከፍታ ገባች።እንደወትሮ ፅድት እንዳለ ነው።እሷ ግን ከወትሮ የተለየ የደመቀና የፈካ እንዲሆን ነበር የፈለገችው።ልቧ ላይ እንደሚንቦገቦገው አይነት የደስታ ብርሀን እቤቱም እንደዛው ይሆናል ብላ ጠብቃ ነበር.. በሚገርም ሁኔታ ግን ምን እንኳን እቤቱ በውስጧ በፈለገችው ሆኔታ ባይሸበርቅም ጠረጰዛው ግን በምትወዳቸው የምግብ አይነቶች ተሞልቶል። ሞባይሏን አወጣችና ከተለያየ አቅጣጫ አንድ ሶስት ፎቶዎች አነሳችና።‹‹እንደውም ጥሩ አጋጣሚ ነው ።እስኪመለስ አንዳንድ ነገሮችን አስተካክላለሁ› ብላ አሰበችና ወደውስጥ ዘለቀች።የቤቱን መብራት አበራችው...ሌላ አነስ ያለች ጠረጰዛ የክፍሉን አንድ ግድግዳ ተጠግታ ትታያለች።የጠረጰዛውን አቅጣጫ አስተካከለችና ያመጣችውን ኬክ መሀከል ላይ አስቀመጠችው.. የውሰኪ ጠርሙሱን አወጣችና ከጎኑ አደረገችው...ዝርግ ሰሀኖችን ፈለገችና ቸኮሌቶቾን በመዘርገፍ ቦታ ሰጠዋቸው ።
‹‹አዎ አሁን የጎደለው ሙዚቃና ቃልዬ ብቻ ነው።››አለችና ሙዚቃ ለመክፈት ወደመኝታ ቤት ገባች።ወደጂፓሱ ሄደችና ሶኬቱን ሰካችው.. እላዩ ላይ ፍላሽ ስለነበረ ከፈተችውና ድምፅን መጥና ወደሳሎን ልትመልስ ስትል አይኗ የቃልን አልጋ ላይ አረፈ..ከተነጠፈው ሰማያዊ የአልጋ ልብስ ላይ ሁለት ነጫጭ ፓስታዎች ተደራርበው ተቀምጠዎል።ለምን እንደሆነ ባይገባትም አልፋቸው መሄድ አልፈለገችም።ወደኃላ ተመለሰችና የአልጋው ጠርዝ ላይ በመቀመጥ አነሳቻቸው፡፡ ሁለቱንም በሁለት እጆቾ ይዛ ከላይ የተፃፈባቸውን አድራሻ አነበበች፡፡
አንደኛው‹‹ከቃል ለጊፋቲ የተፃፈ የስንብት ደብዳቤ ››ይላል።
‹‹የስንብት› ማለት ምን ማለት ነው?።አዎ ገባኝ መድህኔን ልታገባ ስለሆነ እየተሰናታት ነው…።በዚህ መጠን ተበሳጭቶብሻል ማለት ነው..ደግ አደረገ›› አለችና በውስጧ በስኬቶ በመኩራራት ፈነጠዘች፡፡
"እሱን ወደነበረበት አልጋ ላይ ወርወር በማድረግ ሁለተኛውን ገልብጣ፡፡ አድራሻውን ማየት ጀመረች፡፡ በተመሳሳይ ቀለም በአንዳ አይነት የፊደል አጣጣል የተፃፈ ነው፡፡ከቃል ለልዩ የተፃፈ የስንብት ደብዳቤ ይላል፡፡በዚህ ወቅት የቤቱ አየር ተበከለ ፤መተንፈስ ብቻ ሳይሆን አይኖቾን ከፍታ አካባቢዋን ሁሉ ማየት ነው ያቃታት.. ፖስታውን በሚንቀጠቀጡ እጇቾ ቀዳዳ ከፈተችው፡፡
‹ልዩ እንዲህ ያደረኩት አንቺን በአካል አግኝቶ መሰናበት ቀላል ሆኖ ስላላገኘሁት ነው።አንቺና ጊፍቲ ከአባቴ ቀጥሎ በዚህች ምድር ያላችሁኝ የቅርቤም የልቤም ሰዎች ናችሁ።ልዩ እኔ ከአሁን ወዲህ የለውም...እንደምታውቂው ነፍሴ በዚህ አለም ኳኳታና ትርምስ ደስተኛ አይደለችም።ከዚህ በላይ በውስጧ መኳተን ለእኔም ሆነ በዙሪያዬ ላሉ ሰዎች መልካም መስሎ አልታየኝም።ወደእዚህች ምድር የመጣሁበትን ምክንያት ለመመርመር ፀጥታ ወደአረበበትና በፅሞና ማሰላሰል ወደምችልበት ቦታ ማለቴ ወደገዳም አምርቼያለሁ።ነግሬሽ ባላውቅም ወደእዛ መሄድ የረጅም ጊዜ ውጥኔ ነበር...ግን ያው ይህቺ አለም የራሷ የሆነ ወጥመድ አላትና እስከአሁን ሊሳካልኝ አልቻለም ነበር።
ለማንኛውም እግዚያብሄር ነገሮች እንዲከወኑ የሚፈቅድበት የራሱ የሆነ ጊዜ አለው ...እናም ዛሬ ቀኗ ሆነችና ህልሜ ተሳካ።ካዛሬ ጀምሮ እኔ የመንፈሳዊው አለም ምልምል ወታደር ሆኜ ተመርጬለሁ።ጮርቃ የሆነውን መንፈሳዊ ህይወቴንም ጥልቀት ያለው የበሰለና ለሌላው የሚተርፍ እስኪሆን ድረስ በልምምድ ተጋለሁ ሁለት አመትም ፈጀብኝ ሀያ አመት ካልሆነም እድሜ ልክ አያስጨንቀኝም...በመንፈሳዊ ልምምድ ውስጥ ወደ ሰማያዊ ንቃት ለማደግ ምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ።እግዚያብሄርም እንደሚያግዘኝ እተማመናለሁ። አንቺም እንደምትፀልይልኝ ጥርጥር የለኝም።እንግዲህ ልዩ የህይወት አላማዬ አስገድዶኝ በመንፈሳዊ ተልዕኮ ተገድጄ ካልሆነ በስተቀር ከምሄድበት የፅሞናና የፀጥታ ቦታ ወጥቼ ወደእናንተ የምመጣ ስለማይመስለኝ ይህ ስንብት የመጨረሻችን ነው።ግን ደግሞ በሚቀጥለው አለም በተለየ ሁኔታ እንገናኛለን የሚል የፀና እምነት አለኝ።
በስተመጨረሻ ሁለት ነገሮችን እንድታደርጊልኝ እጠይቅሻለሁ ..የመጀመሪያው ለጊፍቲ ጥሩ ጓደኛ እንድትሆኚያትና ሁለተኛው ደግሞ በተቻለሽ መጠን አባቴን እንድትጠይቂው ነው።ያው አንቺም አባት የለሽም አይደል... አባቴን ሸልሜሻለሁ።የቤቱን ዕቃ ከጊፍቲ ጋር ተማክራችሁ እንደሚሆን አድርጉት ወይ ለተቸገረ ስጡት...ብቻ እንደመሠላችሁ። በስተመጨረሻ በእጆቼ ጣቶች በጥልቅ ምስጋናና በፍፅም ፍቅር የመጨረሻ ምሳ አዘጋጅቼልሻለሁ...ጣፍጦሽ እንደምትበይው እርግጠኛ ነኝ።በይ ቻው..እስከአሁን አብረን በቆየንባቸው ጊዜያቶች ስላሳየሽኝ ደግነት፤ስለ ሰጠሸኝ ፍቅር፡ስለአጎናፀፍሽኝ ደስታ ከልቤ አመሰግናለሁ!! አመስገናለሁ!!! አመሰግናለሁ... የእግዜያብሄር መንፈስ በልብሽ ይንገስ.. .አሜን
...እራሷን ተቆጣጥራ ፌንት በልታ ወደኃላዋ ተዘርራ ሳትወድቅ ደብዳቤውን አንብባ ጨረስችው.የዛ አይነት ፅናትና ብርታት ከየት እንዳመጣቸ ለራሷም ደነቃት...ምን እየተሠማት እንደሆነ ማወቅ አልቻለችም።
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
በቀጠሯችን መሰረት ወደቃል ቤት እየሄደች ነው።ይህ ቀጠሮ ለእሷ ልክ እንደከዚ ቀደሞቹ ቀጠሮዎች አይነት አይደለም።ቀጠሮውን ሳታሲዘው እንኳን "ለብቻህ ለረጂም ሰዓት ነው የምፈልግህ..በምንም አይነት የማይሰረዝ የሞት ቀጠሮ ነው"ነበር ያለችው።ልክ ስድስት ሰዓት እሱ ቤት ለመገናኘት ነው የተቀጣጠሩት። ሁለት ሰዓት ከቤት ወጣች፤ የውበት ሳሎን ደንበኞቾ ጋር ሄደች ...ከጥፍሯ አንስቶ ቅንድቧን ፀጉሯን እስክታስተካክልላት አራት ተኩል ሆነ...እቤት ሄዳ በሀገሪቱ አለ በተባለች ዲዛይነር በልዩ ሁኔታ ያሰፋችውን የሀገር በሀል ቀሚስ ለብሳ እሱን ደስ ያሰኘዋል ብላ ባሰችው አለባበስ ዘንጣ መኪናዋን እሱ የሚኖርበት ግቢ አስገብታ ስታቆም ሰዓቱ 6.03 ይል ነበር።የመኪናዋን ሞተር ከጠፋችና ለእለቱ ልዪ ዝግጅት ማድመቂያ ይሆን ዘንድ ይዛ የመጣችውን ቶርታ ኬክ፤ውስኪ፤ሻማዎች እና ቸኮሌቶችን ከእነ ዘንቢሉ እየተንገዳገደችም ቢሆን ይዛ ወረደችና ወደ ቃል ቤት ልትታጠፍ ስትል አሮጊቷ የቤት አከራይ ከእቤታቸው ሲወጡ ተገጣጠሙ ።
"ውይ በጌታ መጣሽ?"አሉ ከሞት የተነሳ ዘመዳቸውን ድንገት እንዳዩ አይነት ደንግጠው። የአሮጊቷ መደንገጥ ብቻ ሳይሆን እንባቸውም እየረገፈ ነው ።
" ማዘር ምን ሆኑ?"
‹‹አረ ምንም አልሆንኩ..ምነው ጠየቅሺኝ?"
"አይ እያለቀሱ ነው ብዬ ነዋ"
"እ አይ ልጄ ጭስ ነገር ነበር ..እቤት ያው ያሮጊት ነገር ታውቂ የለ"
"በሉ እሺ"ብላ መንገዷን ስትቀጥል
"ቆይ ልጄ ቁልፍ ልስጥሸ"አሏትና አስቆሟት፡፡
ውስጧን ክፍት አለው"ምነው ቃል የለም እንዴ?››ለስለስ ባለ ድምፀት ጠየቀቻቸው ።
"ቃል ነው ያልሽው ?"አሉና ወደውስጥ መግባቱን እረስተው ፍዝዝ ብለው ቆሙ፡
"እንዴ እማማ ..ችግር አለ እንዴ?"
"አረ የለም..ማለቴ ቃል ወጣ ብሎ ነው አልቆይም ብሎል"ብለዋት ወደ ውስጥ ገቡ ።
"ቃል ደግሞ በዚህ ቀን?ለዛውም እንዲህ አስጠንቅቄህ"ቃል ስሯ ሆኖ ባይሰማትም ተነጫነጨችበት ።
አሮጊቷ አምጥተው ቁልፍን ሰጧት... ነገረ ስራቸው አላማራትም‹..አይናቸውን ከዓይኔ ለምንድነው የሚያሸሹት?›ቁልፉን ተቀብላ እያልጎመጎመች ወደጓሮ ዞረችና የቃልን ቤት ከፍታ ገባች።እንደወትሮ ፅድት እንዳለ ነው።እሷ ግን ከወትሮ የተለየ የደመቀና የፈካ እንዲሆን ነበር የፈለገችው።ልቧ ላይ እንደሚንቦገቦገው አይነት የደስታ ብርሀን እቤቱም እንደዛው ይሆናል ብላ ጠብቃ ነበር.. በሚገርም ሁኔታ ግን ምን እንኳን እቤቱ በውስጧ በፈለገችው ሆኔታ ባይሸበርቅም ጠረጰዛው ግን በምትወዳቸው የምግብ አይነቶች ተሞልቶል። ሞባይሏን አወጣችና ከተለያየ አቅጣጫ አንድ ሶስት ፎቶዎች አነሳችና።‹‹እንደውም ጥሩ አጋጣሚ ነው ።እስኪመለስ አንዳንድ ነገሮችን አስተካክላለሁ› ብላ አሰበችና ወደውስጥ ዘለቀች።የቤቱን መብራት አበራችው...ሌላ አነስ ያለች ጠረጰዛ የክፍሉን አንድ ግድግዳ ተጠግታ ትታያለች።የጠረጰዛውን አቅጣጫ አስተካከለችና ያመጣችውን ኬክ መሀከል ላይ አስቀመጠችው.. የውሰኪ ጠርሙሱን አወጣችና ከጎኑ አደረገችው...ዝርግ ሰሀኖችን ፈለገችና ቸኮሌቶቾን በመዘርገፍ ቦታ ሰጠዋቸው ።
‹‹አዎ አሁን የጎደለው ሙዚቃና ቃልዬ ብቻ ነው።››አለችና ሙዚቃ ለመክፈት ወደመኝታ ቤት ገባች።ወደጂፓሱ ሄደችና ሶኬቱን ሰካችው.. እላዩ ላይ ፍላሽ ስለነበረ ከፈተችውና ድምፅን መጥና ወደሳሎን ልትመልስ ስትል አይኗ የቃልን አልጋ ላይ አረፈ..ከተነጠፈው ሰማያዊ የአልጋ ልብስ ላይ ሁለት ነጫጭ ፓስታዎች ተደራርበው ተቀምጠዎል።ለምን እንደሆነ ባይገባትም አልፋቸው መሄድ አልፈለገችም።ወደኃላ ተመለሰችና የአልጋው ጠርዝ ላይ በመቀመጥ አነሳቻቸው፡፡ ሁለቱንም በሁለት እጆቾ ይዛ ከላይ የተፃፈባቸውን አድራሻ አነበበች፡፡
አንደኛው‹‹ከቃል ለጊፋቲ የተፃፈ የስንብት ደብዳቤ ››ይላል።
‹‹የስንብት› ማለት ምን ማለት ነው?።አዎ ገባኝ መድህኔን ልታገባ ስለሆነ እየተሰናታት ነው…።በዚህ መጠን ተበሳጭቶብሻል ማለት ነው..ደግ አደረገ›› አለችና በውስጧ በስኬቶ በመኩራራት ፈነጠዘች፡፡
"እሱን ወደነበረበት አልጋ ላይ ወርወር በማድረግ ሁለተኛውን ገልብጣ፡፡ አድራሻውን ማየት ጀመረች፡፡ በተመሳሳይ ቀለም በአንዳ አይነት የፊደል አጣጣል የተፃፈ ነው፡፡ከቃል ለልዩ የተፃፈ የስንብት ደብዳቤ ይላል፡፡በዚህ ወቅት የቤቱ አየር ተበከለ ፤መተንፈስ ብቻ ሳይሆን አይኖቾን ከፍታ አካባቢዋን ሁሉ ማየት ነው ያቃታት.. ፖስታውን በሚንቀጠቀጡ እጇቾ ቀዳዳ ከፈተችው፡፡
‹ልዩ እንዲህ ያደረኩት አንቺን በአካል አግኝቶ መሰናበት ቀላል ሆኖ ስላላገኘሁት ነው።አንቺና ጊፍቲ ከአባቴ ቀጥሎ በዚህች ምድር ያላችሁኝ የቅርቤም የልቤም ሰዎች ናችሁ።ልዩ እኔ ከአሁን ወዲህ የለውም...እንደምታውቂው ነፍሴ በዚህ አለም ኳኳታና ትርምስ ደስተኛ አይደለችም።ከዚህ በላይ በውስጧ መኳተን ለእኔም ሆነ በዙሪያዬ ላሉ ሰዎች መልካም መስሎ አልታየኝም።ወደእዚህች ምድር የመጣሁበትን ምክንያት ለመመርመር ፀጥታ ወደአረበበትና በፅሞና ማሰላሰል ወደምችልበት ቦታ ማለቴ ወደገዳም አምርቼያለሁ።ነግሬሽ ባላውቅም ወደእዛ መሄድ የረጅም ጊዜ ውጥኔ ነበር...ግን ያው ይህቺ አለም የራሷ የሆነ ወጥመድ አላትና እስከአሁን ሊሳካልኝ አልቻለም ነበር።
ለማንኛውም እግዚያብሄር ነገሮች እንዲከወኑ የሚፈቅድበት የራሱ የሆነ ጊዜ አለው ...እናም ዛሬ ቀኗ ሆነችና ህልሜ ተሳካ።ካዛሬ ጀምሮ እኔ የመንፈሳዊው አለም ምልምል ወታደር ሆኜ ተመርጬለሁ።ጮርቃ የሆነውን መንፈሳዊ ህይወቴንም ጥልቀት ያለው የበሰለና ለሌላው የሚተርፍ እስኪሆን ድረስ በልምምድ ተጋለሁ ሁለት አመትም ፈጀብኝ ሀያ አመት ካልሆነም እድሜ ልክ አያስጨንቀኝም...በመንፈሳዊ ልምምድ ውስጥ ወደ ሰማያዊ ንቃት ለማደግ ምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ።እግዚያብሄርም እንደሚያግዘኝ እተማመናለሁ። አንቺም እንደምትፀልይልኝ ጥርጥር የለኝም።እንግዲህ ልዩ የህይወት አላማዬ አስገድዶኝ በመንፈሳዊ ተልዕኮ ተገድጄ ካልሆነ በስተቀር ከምሄድበት የፅሞናና የፀጥታ ቦታ ወጥቼ ወደእናንተ የምመጣ ስለማይመስለኝ ይህ ስንብት የመጨረሻችን ነው።ግን ደግሞ በሚቀጥለው አለም በተለየ ሁኔታ እንገናኛለን የሚል የፀና እምነት አለኝ።
በስተመጨረሻ ሁለት ነገሮችን እንድታደርጊልኝ እጠይቅሻለሁ ..የመጀመሪያው ለጊፍቲ ጥሩ ጓደኛ እንድትሆኚያትና ሁለተኛው ደግሞ በተቻለሽ መጠን አባቴን እንድትጠይቂው ነው።ያው አንቺም አባት የለሽም አይደል... አባቴን ሸልሜሻለሁ።የቤቱን ዕቃ ከጊፍቲ ጋር ተማክራችሁ እንደሚሆን አድርጉት ወይ ለተቸገረ ስጡት...ብቻ እንደመሠላችሁ። በስተመጨረሻ በእጆቼ ጣቶች በጥልቅ ምስጋናና በፍፅም ፍቅር የመጨረሻ ምሳ አዘጋጅቼልሻለሁ...ጣፍጦሽ እንደምትበይው እርግጠኛ ነኝ።በይ ቻው..እስከአሁን አብረን በቆየንባቸው ጊዜያቶች ስላሳየሽኝ ደግነት፤ስለ ሰጠሸኝ ፍቅር፡ስለአጎናፀፍሽኝ ደስታ ከልቤ አመሰግናለሁ!! አመስገናለሁ!!! አመሰግናለሁ... የእግዜያብሄር መንፈስ በልብሽ ይንገስ.. .አሜን
...እራሷን ተቆጣጥራ ፌንት በልታ ወደኃላዋ ተዘርራ ሳትወድቅ ደብዳቤውን አንብባ ጨረስችው.የዛ አይነት ፅናትና ብርታት ከየት እንዳመጣቸ ለራሷም ደነቃት...ምን እየተሠማት እንደሆነ ማወቅ አልቻለችም።
✨ይቀጥላል✨
👍143❤20🤔11👎8🥰2😁1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹የትናንቶቹን ልጆች ሙሉ ታሪክ ማወቅ እፈለጋለሁ››ለንስሯ ነው እየነገረችው
‹‹ይቻላል››መለሰለት ዛፉ ላይ ሆኖ
‹‹በቃ አሁን ዝናቡ ሊዘንብ ነው …ዝናቡ ሲያባራ ታጣራልኛለህ››
በእሷ በማሾፍ በሚመስል ሁኔታ ክንፉን አርገፈገፈ…እሷ እንዲህ ያለችው ግቢዋ ውሰጥ ያሉ አዕዋፋት ዝናቡን ሽሽት በየዛፎቹ ቅርንጫፎች ሲሸሸጉ እና ወደጎጆቸው ሲገቡ ..ዝንጀሮዋችና ጉሬዛዎቾ ወደመጣለያቸው ሲሸጎጡ አይታ… እሷም ውሽንፍሩን በመፍራት ወደቤት ልትገባ መነሳቷን ከግምት በማስገባት ንስሯም እየዘነበ ካለው ዝናብ ለመጠለል አብሮኝ ተከትሎ ወደቤት ይገባል በሚል ግምት ነው…..በሀሳብ ውስጥ ሆና በዝንጉነት ያሰበችው ሀሳብ
ለካ ንስር ነው…
ንሰሯ አይኖ እያየ ወደላይ ተምዘገዘገ .እያነሰ እያነሰ ደመናውን ሰንጥቆ ከአይኗ ተሰወረ ….አዎ ከደመናው በላይ ብቻ ሳይሆን ከሚዘንበውም ዝናብም በላይ ነው የሆነው..እሷ ዝናብን ስትጠለል ንስሯ ንፍስ የቀላቀለውን ውሽንፍር እየሰነጠቀ በኩራትና በአሸናፊነት ከተዘረጋው ደመና እና ከሚረግፈው ዝናብ በላይ በመምጠቅ ቁልቁል እያየ ሊዝናናበት..
በንስሯ ሁኔታ ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ገባች…..ቁርስ ልታበስል አስባ ነበር …ግን ምንም አይነት የምግብ ፈልጎት ስለሌላት ወደመኝታ ክፍሏ ገባችና መልሳ አልጋዋ ላይ ወጣች..አዎ በዝናብ መኝታ ውስጥ ሆኖ ማሰብ ወይም ሙዚቃ ማዳመጥ የሚያስደስታት ነገር ነው…
‹‹እስቲ ንስሬ ስለትናንቱ ባሪያ ልጅ እና በቅርቡ ሟች ስለምትሆነው ፍቅረኛው ምን አይነት ታሪክ ይዞልኝ ይመጣ ይሆን ……….?የልጅቷስ የማይድነው በሽታዋስ ምን ይሆን….?እንድትሞት ልተዋት ..ወይስ ከንስሬ ጋር ሆኜ ላድናት……….?ቆይ እሱ እንደታሪካቸው ሁኔታ ነው የሚወሰነው….አሁን ንስሬ ከቅኝት ሲመለስ ልክ እንደተካታታይ የሆሊውድ ፊልም ታሪካቸውን ይዘረግፍልኛል….››
ምክንያቱን ባታውቅም ንስሯ ካሰበችው በላይ ቆየባት፡፡
ቆይ ቆይ እስኪ ድምጽ ይሰማኛል………….
ገርበብ ያለው መኝታ ቤት ተበረግዶ ተከፈተ…ሌላ ሰው አይደለም ንስሯ ነው….በራፉን በመንቁሩ ስቦ በመበርገድ በሮ አልጋዋ ላይ ከጎኗ ጉብ ያለው… ክንፎቹን ወደ ውስጥ ሰብስቦ አንገቱን ቀብሮ ሽብልል ብሎ ተኛ…ጥሩ ነገር ይዞላት እንዳልመጣ ገባት…ሁልጊዜ የሆነ ነገር እንዲያጣራላት ልካው ያገኘው መረጃ አና ከምፈልገው በተቃራኒ ከሆነ እንዲህ ነው ዝልፍልፍ የሚለው…ዝልፍልፍ ማለት ደግሞ በእሱ አያምርም፡፡
የንስሯን ሁኔታ ሰለልጁ ታሪክ ለማወቅ ያለቻትን ጉጉት በእጥፍ ጨመረበት..እራሷን አስተካክላ ሀሳቧን ሰብስባ ወደንስሯ አዕምሮ ዘልቃ ገባች..ያየውን ለማየት…ያወቀውን ለማወቅ
//
የትናንትናው ቀልቧን ሰልቧት የነበረው ባሪያው ልጅ መላኩ ይባላል ..እሷ ማለት ከሞት ጋር ቀጠሮ ይዛ በስጋት ኑሮ ላይ ያለችው ፍቅረኛው ስም ደግሞ ሰሚራ ትባላለች…ሁለቱ የተገናኙት ከአራት አመት በፊት ነው….
ንስሯም ስለሁለቱ ፍቅረኛሞች ይዞላት የመጣው ታሪክ መነሻው ከተገናኙበት የዛሬ አራት አመት ወዲህ ያለውን ነው……
አዎ ሰሚራ ነርስ ነች …በአንድ የግል ሆስፒታል ውስጥ በነርስነት በምትሰራበት እና ተረኛ ሆና የስራ ገበታው ላይ በነበረችበት በአንድ ቀን ከ4 ዓመት በፊት ማለት ነው፡፡አንድ ወጣት በሞት እና በህይወት መካከል ተንጠልጥሎ አረፋ ደፍቆ እያቃተተ በአንብላንስ ተጭኖ ይመጣል..
አጋጣሚ ሆኖ በዕለቱ ሰሚራ ተረኛ እንደመሆኗ መጠን ከሌሎች ዶክተሮች ጋር ሆና የመጣውን በሽታኛ ህይወት ለማትረፍ ባለአቅማቸው እና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም ይሯሯጣሉ…. ወጣቱ ኃይለኛ ገዳይ መርዝ በመላ ሰውነቱን ተሰራጭቶ አንጀቱን እየበጣጠሰው ነበር ....ከዛ በእነሱ ጥረት የእግዜርም በጎ ፍቃድ ተጨምሮበት ከመሞት ይተራፋል… ግን ጉዳቱ ከፍተኛ ስለነበር ከገባበት ኮማ ለመንቃት አልቻለም ነበር….ስለሆነም የጤናው ሁኔታ በአስተማማኝ ሁኔታ እስኪስተካከል እዛው ሆስፒታል ተኝቶ ክትትል እንዲያደርግ ይወሰናል…
ያ ወጣት ሆስፒታል ከገባበት ቀን አንስቶ አብረውት የነበሩ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ ጎልማሶች ነበሩ….ሰሚራ በወቅቱ ከእነሱ ከራሳቸው ጠይቃ እንደተረዳችው ሴቷ የበሽተኛው ፍቅረኛ ወንዱ ደግሞ በአባት የሚገናኘው ግማሽ ወንድሙ …..….በተጨማሪም ፖሊሶችም ገባ ወጣ ይሉ ነበር…የበሽተኛውን መንቃት ተከትሎ የሚሰጠውን ቃል ለመቀበል…
እሷም ምንም እንኳን የስራዋ አንዱ ግዳጅ እና ኃላፊቷ ቢሆንም ግን በማታውቀው ሌላ ተጨማሪ የተለየ ስሜት እየተገፋፋች በከፍተኛ ሁኔታ ስትንከባከበው ትቆያለች…አብረውት የሚያሰትምሙት ቤተሰቦቹ እስኪገረሙባት ድረስ፡፡በሽተኛው እስከ ሶስተኛው ቀን ድረስ ከገባበት ኮማ መንቃት አልቻለም ነበር ፤በአራተኛው ቀን ግን ለ5 ደቂቃ ያህል አይኖቹን መግለጥ እና አንደበቱን ማላቀቅ ቻለ..የመዳን ተስፋው በእጥፍ ጨመረ፤ይሄ ሁኔታ ሰሚራን እና ጓደኞቾን በጣም ቢያስደስታቸውም የመላኩን አሰታማሚ ቤተሰቦች ግን በሚገርም ሁኔታ አለመረጋጋት እና ድንጋጤ ውስጥ ከተታቸው፤ይህንንም ጉዳይ ሰሚራ መታዘብ ስለቻለች ግራ ተጋብታ ትዝብቷን በውስጧ ቀብራ ስትብሰለሰል ትሰነብታለች፤በአምስተኛው ቀን ግን ሰሚራ የእለት ስራዋን አጠናቃ ወደቤቷ ስትመለስ የመላኩ አስታማሚዎች እቤቷ በራፍ ላይ ቆመው ሲጠብቋት አገኘች
ሰሚራም ደንግጣ‹‹ምን ተፈጠረ..….?ምን እግር ጣላችሁ….?››
ሰላም ምትባለው…የመላኩ እጮኛ‹‹ተረጋጊ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነው….?››አለቻት፡፡
‹‹ምንድነው ምታማክሩኝ …….?ደግሞስ ሆስፒታል ተገናኝተን አልነበር..እዛው እኮ ልትጠይቁኝ ትችሉ ነበር…?››
የበሽተኛው ግማሽ ወንድም የሆነው ሰሎሞን‹‹አይ እዛማ በስራ ወከባ ላይ ስለሆንሽ የግል ጉዳይ ለማውራት አይመችም ብለን ነው››
ግራ ትጋባና ‹‹የግል ጉዳይ …….?ማለት ስለ መላኩ ጤንነት ማለታችሁ ነው….?›› ብላ ጠየቀች…ሌላ ከእሷ ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ አልታይሽ ብሏት፡፡
ሰላም እያቅማማች ‹‹አዎ ግን ካላስቸገርንሽ ወይ እቤትሽ ገብተን ወይ ደግሞ ሌላ ቦታ ሄደን ብናናግርሽ››
ሰሚራ ምታደርገውም ምትናገረውም ግራ ገብቷት ወደ ቤቷ ይዛቸው ትገባለች…ወደቤት ከገቡ በኃላ ለውይይት ያቀረቡላት ርዕስ ከጠበቀችው በጣም የራቀና አስደንጋጭ ነበር…››
የግማሽ ሚሊዬን ብር ቼክ በእጇ ላይ ካስቀመጡላት በኃላ ….‹‹መላኩን እንዳይድን አድርጊልን››ነበር ያሏት፡፡
‹‹እንዴ ለምን…….?ለአንቺ ፍቅረኛሽ ለአንተ ደግሞ ወንድምህ አይደል…….?ነው ወይስ ዋሽታችሁኛል….?፡፡››
‹‹አይ እሱን አልዋሸንሽም…ግን አንቺ ማይገባሽ ብዙ ጉዳዬች አሉ..አሁን ብታድኝው እራሱ ሙሉ ጤነኛ አይሆንም ..አካሉ እንደልብ ላይታዘዝለት ይችላል..ወይም አዕምሮው የማሰብ አቅሙ ተዛብቶ ዘገምተኛ ሆኖ ሊቀር ይችላል….እንደዛ የመሆን እድል እንደሚገጥመው ደግሞ የነገራችሁን እናንተው ናችሁ፡፡››
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹የትናንቶቹን ልጆች ሙሉ ታሪክ ማወቅ እፈለጋለሁ››ለንስሯ ነው እየነገረችው
‹‹ይቻላል››መለሰለት ዛፉ ላይ ሆኖ
‹‹በቃ አሁን ዝናቡ ሊዘንብ ነው …ዝናቡ ሲያባራ ታጣራልኛለህ››
በእሷ በማሾፍ በሚመስል ሁኔታ ክንፉን አርገፈገፈ…እሷ እንዲህ ያለችው ግቢዋ ውሰጥ ያሉ አዕዋፋት ዝናቡን ሽሽት በየዛፎቹ ቅርንጫፎች ሲሸሸጉ እና ወደጎጆቸው ሲገቡ ..ዝንጀሮዋችና ጉሬዛዎቾ ወደመጣለያቸው ሲሸጎጡ አይታ… እሷም ውሽንፍሩን በመፍራት ወደቤት ልትገባ መነሳቷን ከግምት በማስገባት ንስሯም እየዘነበ ካለው ዝናብ ለመጠለል አብሮኝ ተከትሎ ወደቤት ይገባል በሚል ግምት ነው…..በሀሳብ ውስጥ ሆና በዝንጉነት ያሰበችው ሀሳብ
ለካ ንስር ነው…
ንሰሯ አይኖ እያየ ወደላይ ተምዘገዘገ .እያነሰ እያነሰ ደመናውን ሰንጥቆ ከአይኗ ተሰወረ ….አዎ ከደመናው በላይ ብቻ ሳይሆን ከሚዘንበውም ዝናብም በላይ ነው የሆነው..እሷ ዝናብን ስትጠለል ንስሯ ንፍስ የቀላቀለውን ውሽንፍር እየሰነጠቀ በኩራትና በአሸናፊነት ከተዘረጋው ደመና እና ከሚረግፈው ዝናብ በላይ በመምጠቅ ቁልቁል እያየ ሊዝናናበት..
በንስሯ ሁኔታ ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ገባች…..ቁርስ ልታበስል አስባ ነበር …ግን ምንም አይነት የምግብ ፈልጎት ስለሌላት ወደመኝታ ክፍሏ ገባችና መልሳ አልጋዋ ላይ ወጣች..አዎ በዝናብ መኝታ ውስጥ ሆኖ ማሰብ ወይም ሙዚቃ ማዳመጥ የሚያስደስታት ነገር ነው…
‹‹እስቲ ንስሬ ስለትናንቱ ባሪያ ልጅ እና በቅርቡ ሟች ስለምትሆነው ፍቅረኛው ምን አይነት ታሪክ ይዞልኝ ይመጣ ይሆን ……….?የልጅቷስ የማይድነው በሽታዋስ ምን ይሆን….?እንድትሞት ልተዋት ..ወይስ ከንስሬ ጋር ሆኜ ላድናት……….?ቆይ እሱ እንደታሪካቸው ሁኔታ ነው የሚወሰነው….አሁን ንስሬ ከቅኝት ሲመለስ ልክ እንደተካታታይ የሆሊውድ ፊልም ታሪካቸውን ይዘረግፍልኛል….››
ምክንያቱን ባታውቅም ንስሯ ካሰበችው በላይ ቆየባት፡፡
ቆይ ቆይ እስኪ ድምጽ ይሰማኛል………….
ገርበብ ያለው መኝታ ቤት ተበረግዶ ተከፈተ…ሌላ ሰው አይደለም ንስሯ ነው….በራፉን በመንቁሩ ስቦ በመበርገድ በሮ አልጋዋ ላይ ከጎኗ ጉብ ያለው… ክንፎቹን ወደ ውስጥ ሰብስቦ አንገቱን ቀብሮ ሽብልል ብሎ ተኛ…ጥሩ ነገር ይዞላት እንዳልመጣ ገባት…ሁልጊዜ የሆነ ነገር እንዲያጣራላት ልካው ያገኘው መረጃ አና ከምፈልገው በተቃራኒ ከሆነ እንዲህ ነው ዝልፍልፍ የሚለው…ዝልፍልፍ ማለት ደግሞ በእሱ አያምርም፡፡
የንስሯን ሁኔታ ሰለልጁ ታሪክ ለማወቅ ያለቻትን ጉጉት በእጥፍ ጨመረበት..እራሷን አስተካክላ ሀሳቧን ሰብስባ ወደንስሯ አዕምሮ ዘልቃ ገባች..ያየውን ለማየት…ያወቀውን ለማወቅ
//
የትናንትናው ቀልቧን ሰልቧት የነበረው ባሪያው ልጅ መላኩ ይባላል ..እሷ ማለት ከሞት ጋር ቀጠሮ ይዛ በስጋት ኑሮ ላይ ያለችው ፍቅረኛው ስም ደግሞ ሰሚራ ትባላለች…ሁለቱ የተገናኙት ከአራት አመት በፊት ነው….
ንስሯም ስለሁለቱ ፍቅረኛሞች ይዞላት የመጣው ታሪክ መነሻው ከተገናኙበት የዛሬ አራት አመት ወዲህ ያለውን ነው……
አዎ ሰሚራ ነርስ ነች …በአንድ የግል ሆስፒታል ውስጥ በነርስነት በምትሰራበት እና ተረኛ ሆና የስራ ገበታው ላይ በነበረችበት በአንድ ቀን ከ4 ዓመት በፊት ማለት ነው፡፡አንድ ወጣት በሞት እና በህይወት መካከል ተንጠልጥሎ አረፋ ደፍቆ እያቃተተ በአንብላንስ ተጭኖ ይመጣል..
አጋጣሚ ሆኖ በዕለቱ ሰሚራ ተረኛ እንደመሆኗ መጠን ከሌሎች ዶክተሮች ጋር ሆና የመጣውን በሽታኛ ህይወት ለማትረፍ ባለአቅማቸው እና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም ይሯሯጣሉ…. ወጣቱ ኃይለኛ ገዳይ መርዝ በመላ ሰውነቱን ተሰራጭቶ አንጀቱን እየበጣጠሰው ነበር ....ከዛ በእነሱ ጥረት የእግዜርም በጎ ፍቃድ ተጨምሮበት ከመሞት ይተራፋል… ግን ጉዳቱ ከፍተኛ ስለነበር ከገባበት ኮማ ለመንቃት አልቻለም ነበር….ስለሆነም የጤናው ሁኔታ በአስተማማኝ ሁኔታ እስኪስተካከል እዛው ሆስፒታል ተኝቶ ክትትል እንዲያደርግ ይወሰናል…
ያ ወጣት ሆስፒታል ከገባበት ቀን አንስቶ አብረውት የነበሩ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ ጎልማሶች ነበሩ….ሰሚራ በወቅቱ ከእነሱ ከራሳቸው ጠይቃ እንደተረዳችው ሴቷ የበሽተኛው ፍቅረኛ ወንዱ ደግሞ በአባት የሚገናኘው ግማሽ ወንድሙ …..….በተጨማሪም ፖሊሶችም ገባ ወጣ ይሉ ነበር…የበሽተኛውን መንቃት ተከትሎ የሚሰጠውን ቃል ለመቀበል…
እሷም ምንም እንኳን የስራዋ አንዱ ግዳጅ እና ኃላፊቷ ቢሆንም ግን በማታውቀው ሌላ ተጨማሪ የተለየ ስሜት እየተገፋፋች በከፍተኛ ሁኔታ ስትንከባከበው ትቆያለች…አብረውት የሚያሰትምሙት ቤተሰቦቹ እስኪገረሙባት ድረስ፡፡በሽተኛው እስከ ሶስተኛው ቀን ድረስ ከገባበት ኮማ መንቃት አልቻለም ነበር ፤በአራተኛው ቀን ግን ለ5 ደቂቃ ያህል አይኖቹን መግለጥ እና አንደበቱን ማላቀቅ ቻለ..የመዳን ተስፋው በእጥፍ ጨመረ፤ይሄ ሁኔታ ሰሚራን እና ጓደኞቾን በጣም ቢያስደስታቸውም የመላኩን አሰታማሚ ቤተሰቦች ግን በሚገርም ሁኔታ አለመረጋጋት እና ድንጋጤ ውስጥ ከተታቸው፤ይህንንም ጉዳይ ሰሚራ መታዘብ ስለቻለች ግራ ተጋብታ ትዝብቷን በውስጧ ቀብራ ስትብሰለሰል ትሰነብታለች፤በአምስተኛው ቀን ግን ሰሚራ የእለት ስራዋን አጠናቃ ወደቤቷ ስትመለስ የመላኩ አስታማሚዎች እቤቷ በራፍ ላይ ቆመው ሲጠብቋት አገኘች
ሰሚራም ደንግጣ‹‹ምን ተፈጠረ..….?ምን እግር ጣላችሁ….?››
ሰላም ምትባለው…የመላኩ እጮኛ‹‹ተረጋጊ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነው….?››አለቻት፡፡
‹‹ምንድነው ምታማክሩኝ …….?ደግሞስ ሆስፒታል ተገናኝተን አልነበር..እዛው እኮ ልትጠይቁኝ ትችሉ ነበር…?››
የበሽተኛው ግማሽ ወንድም የሆነው ሰሎሞን‹‹አይ እዛማ በስራ ወከባ ላይ ስለሆንሽ የግል ጉዳይ ለማውራት አይመችም ብለን ነው››
ግራ ትጋባና ‹‹የግል ጉዳይ …….?ማለት ስለ መላኩ ጤንነት ማለታችሁ ነው….?›› ብላ ጠየቀች…ሌላ ከእሷ ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ አልታይሽ ብሏት፡፡
ሰላም እያቅማማች ‹‹አዎ ግን ካላስቸገርንሽ ወይ እቤትሽ ገብተን ወይ ደግሞ ሌላ ቦታ ሄደን ብናናግርሽ››
ሰሚራ ምታደርገውም ምትናገረውም ግራ ገብቷት ወደ ቤቷ ይዛቸው ትገባለች…ወደቤት ከገቡ በኃላ ለውይይት ያቀረቡላት ርዕስ ከጠበቀችው በጣም የራቀና አስደንጋጭ ነበር…››
የግማሽ ሚሊዬን ብር ቼክ በእጇ ላይ ካስቀመጡላት በኃላ ….‹‹መላኩን እንዳይድን አድርጊልን››ነበር ያሏት፡፡
‹‹እንዴ ለምን…….?ለአንቺ ፍቅረኛሽ ለአንተ ደግሞ ወንድምህ አይደል…….?ነው ወይስ ዋሽታችሁኛል….?፡፡››
‹‹አይ እሱን አልዋሸንሽም…ግን አንቺ ማይገባሽ ብዙ ጉዳዬች አሉ..አሁን ብታድኝው እራሱ ሙሉ ጤነኛ አይሆንም ..አካሉ እንደልብ ላይታዘዝለት ይችላል..ወይም አዕምሮው የማሰብ አቅሙ ተዛብቶ ዘገምተኛ ሆኖ ሊቀር ይችላል….እንደዛ የመሆን እድል እንደሚገጥመው ደግሞ የነገራችሁን እናንተው ናችሁ፡፡››
👍70😱8❤4🥰1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፎዚያ ኤልያስን ደውሎ መልዕክቱን እንደነገራት ጥዋት ወደ ሀዋሳ ለመሄድ መያዝ ያለባትን ዕቃዎች ካሰናዳች በኃላ በለሊት ለመነሳት በጊዜ መተኛት ስላለባት ወደ መኝታዋ አመራች፡፡ ግን አንድ የረሳችው ነገር ትዝ አላት፡፡ ለሰሎሞን ደውላ ትንግርት መታሰሯን ልትነግረው ይገባል፡፡ካለዛ ይቀየማል፡፡ በቤት ስልክ ደወለችለት፡፡
‹‹እሺ ሰሎሞን እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ..ምነው በምሽት ደወልሽ?››
‹‹አይ በሰላም ነው ፡፡አንተ ግን ቤት አይደለህም መሰለኝ ..የሆነ ንፋስ ነገር ይሰማኛል ፡፡››
‹‹ሆስፒታል ነኝ ባክሽ፡፡››
‹‹ምነው? ምን ትሰራለህ?››በድንጋጤ ጠየቀችው፡፡
‹‹ኤደንን አሟት ጋንዲ ነው ያለነው፡፡››
‹‹እንዴ!! ቀኗ ደረሷል እንዴ?››
‹‹ኧረ እንደኛ አቆጣጠር አንድ ወር ገደማ ይቀራታል፡፡››
‹‹ታዲያ ምነው?››
‹‹እኔ እንጃ ባክሽ.. ገና ምርመራ ላይ ነች... ውጤቱን አላወቅንም፡፡››
‹‹አይዞህ ምንም አትሆንም፡፡ እግዚር ይማርልህ፤ነገ እጠይቃታለሁ፤ደህና እደር፡፡››
‹‹እንዴ ..ለምን እንደፈለግሺኝ እኮ አልነገርሺኝም?››
‹‹ምንም ጉዳይ የለኝም፤ ዝም ብዬ ለሰላምታ ነው የደወልኩልህ›› አለችው... እንዲህ በችግር ላይ እያለ ስለትንግርት ነግራው ይበልጥ ልታስጨንቀው አልፈለገችም፡፡
‹‹በዚህ ሰዓት ለሰላምታ ..?አድርገሽ የማታውቂውን፤.ይልቅ ቶሎ ንገሪኝ…?ምነው ችግር አለ ?ሁሴን ደውሎ ነበር እንዴ?››
<<ችግር የለም ሁሉም ነገር ሰላም ነው፤በል ቻው፡፡››ብላ ዘጋችበት እና የስልኩን እጄታ ወደ ቦታው መልሳ ወደ መኝታዋ አመራች፡፡
ሰሎሞን ትከሻውን ቀፈፈው፡፡የሆነ ነገር እንደተከሰተ ጠረጠረ፣ ‹በሰላምማ በዚህ ሰዓት አትደውልልኝም፡፡ ቀድሜ የእሷን ጉዳይ መስማት ሲገባኝ የራሴን ችግር ስነግራት ነው ሀሳቧን የቀየረችው፡፡››ሲል አሰበ፡፡ ለማጣራት ትንግርት ጋር ደወለ …ጥሪ አይቀበልም ይላል…፡፡
መልሶ ፎዚያ ጋ ደወለ ...አታነሳም ፤ በቤቱ ስልክ ሞከረ አይነሳም፡፡ለጊዜው ሀሳቡን ሰበሰበና ሚስቱ ወደ ተኛችበት ክፍል አመራ.. እንዴት እንደሆነች ለማየት፡፡
ፎዚያ እንቅልፍ እንዲወስዳት ብትመኝም ከመገላበጥ ውጭ ሊሳካላት አልቻለም፡፡ሰባት ሰዓት ላይ ሞባይሏ ጮኸ ...ሰሎሞን መስሏት ችላ ልትለው ነበር ፡፡በተጨናበሰ ዓይኗ አጨንቁራ ስታየው ግን የውጭ ስልክ ነው ..ተስፈንጥራ አነሳችው፡፡
‹‹ሄሎ ፎዚ፡፡››ሁሴን ነበር የደወለላት፡፡
‹‹ሄሎ ሁስን..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ፡፡ የትንግርት ስልክ አይሰራም… እስቲ አገናኚኝ?››
ደነገጠች ምን ትበለው‹‹የለችም፡፡››
‹‹የት ሄደች?››
‹‹ለስራ..ማለቴ... ከኤልያስ ጋር ሀዋሳ፡፡›› ተንተባተበችበት፡፡
‹‹ፎዚ እኔ በደንብ አውቅሻለሁ፤አንቺ ውሸት አትችይበትም...የሆነውን ንገሪኝ?››
‹‹እውነቴን ነው ሀዋሳ ነው የሄደችው፡፡››
‹‹ታዲያ ስልኳን ለምን ዘጋች?››
አመለጣት‹‹ታስራ ነው››
<<ምን!?>>
‹‹አዎ..እኔም ግራ ገብቶኛል...የሆነች አንድ ሴት በጠርሙስ ፈንክታ ነው አሉ የታሰረችው፡፡››
‹‹የምን ሴት…? በምን ተጣልተው?››
‹‹በምን እንደተጣሉ እስከአሁን አልታወቀም፡፡››
‹‹ማነች ሴትዬዋ?››
‹‹አላወቅኳትም...በቅርብ ከአሜሪካ የመጣች ዲያስፖራ ነች አሉ፡፡የሆነ የእርዳታ ድርጅት ውስጥ እንደምትሰራም ሰምቼያለው፡፡››
‹‹ስሟ ማን ነው?››
‹‹ውይ ስሟን አላውቅም?››
‹‹በይ ከአስር ደቂቃ በኃላ ደውላለሁ.. አጣርተሸ ጠብቂኝ፡፡›› ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ እንዳለው በ11 ደኛው ደቂቃ ደወለ፡፡
‹‹እሺ ፎዚ ምን አገኘሽ?››
‹‹ዶ/ር ሶፊያ ይድነቃቸው ትባላለች፡፡››መረጃውን ከኤልያስ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹ዶክተር ሶፊያ!!!?››
ይበልጥ አርበተበታት‹‹ አዎ ዶ/ር ሶፊያ… ምነው ታውቃታለህ?››
‹‹አዎ... ትንግርት ስለእሷ ነግራኛለች፡፡››
‹‹የት ነው የሚተዋወቁት?››
‹‹በጣም የሚዋደዱ ጓደኛሞች ነበሩ››አለ ፃረሞት ባረበበበት የሰለለ ድምፅ፡፡
ፎዚያ ከድንጋጤው የተነሳ መቃዠት የጀመረች መሰላት ‹‹ዶ/ር ሶፊያ እኮ ነው ያልኩህ ...፤የምን......................
‹‹ተይው ፎዚ፤ ከባድ አደጋ ላይ ነን ያለነው፤በቃ ቻው ነገ እደውልልሻለሁ›› ብሎ ስልኩን አቆረጠው፡፡
ፎዚያም እንደፈዘዘች ከድምፅ አልባው ሞባይሏ ጋር ተፋጣ ቀረች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ 5 ሰው #subscribe ካደረገ ቀጣዩ ክፍል ማታ 3 ሰአት ላይ ይለቀቃል ዛሬ ከተሳካ እሞክራለው !!
#Share and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፎዚያ ኤልያስን ደውሎ መልዕክቱን እንደነገራት ጥዋት ወደ ሀዋሳ ለመሄድ መያዝ ያለባትን ዕቃዎች ካሰናዳች በኃላ በለሊት ለመነሳት በጊዜ መተኛት ስላለባት ወደ መኝታዋ አመራች፡፡ ግን አንድ የረሳችው ነገር ትዝ አላት፡፡ ለሰሎሞን ደውላ ትንግርት መታሰሯን ልትነግረው ይገባል፡፡ካለዛ ይቀየማል፡፡ በቤት ስልክ ደወለችለት፡፡
‹‹እሺ ሰሎሞን እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ..ምነው በምሽት ደወልሽ?››
‹‹አይ በሰላም ነው ፡፡አንተ ግን ቤት አይደለህም መሰለኝ ..የሆነ ንፋስ ነገር ይሰማኛል ፡፡››
‹‹ሆስፒታል ነኝ ባክሽ፡፡››
‹‹ምነው? ምን ትሰራለህ?››በድንጋጤ ጠየቀችው፡፡
‹‹ኤደንን አሟት ጋንዲ ነው ያለነው፡፡››
‹‹እንዴ!! ቀኗ ደረሷል እንዴ?››
‹‹ኧረ እንደኛ አቆጣጠር አንድ ወር ገደማ ይቀራታል፡፡››
‹‹ታዲያ ምነው?››
‹‹እኔ እንጃ ባክሽ.. ገና ምርመራ ላይ ነች... ውጤቱን አላወቅንም፡፡››
‹‹አይዞህ ምንም አትሆንም፡፡ እግዚር ይማርልህ፤ነገ እጠይቃታለሁ፤ደህና እደር፡፡››
‹‹እንዴ ..ለምን እንደፈለግሺኝ እኮ አልነገርሺኝም?››
‹‹ምንም ጉዳይ የለኝም፤ ዝም ብዬ ለሰላምታ ነው የደወልኩልህ›› አለችው... እንዲህ በችግር ላይ እያለ ስለትንግርት ነግራው ይበልጥ ልታስጨንቀው አልፈለገችም፡፡
‹‹በዚህ ሰዓት ለሰላምታ ..?አድርገሽ የማታውቂውን፤.ይልቅ ቶሎ ንገሪኝ…?ምነው ችግር አለ ?ሁሴን ደውሎ ነበር እንዴ?››
<<ችግር የለም ሁሉም ነገር ሰላም ነው፤በል ቻው፡፡››ብላ ዘጋችበት እና የስልኩን እጄታ ወደ ቦታው መልሳ ወደ መኝታዋ አመራች፡፡
ሰሎሞን ትከሻውን ቀፈፈው፡፡የሆነ ነገር እንደተከሰተ ጠረጠረ፣ ‹በሰላምማ በዚህ ሰዓት አትደውልልኝም፡፡ ቀድሜ የእሷን ጉዳይ መስማት ሲገባኝ የራሴን ችግር ስነግራት ነው ሀሳቧን የቀየረችው፡፡››ሲል አሰበ፡፡ ለማጣራት ትንግርት ጋር ደወለ …ጥሪ አይቀበልም ይላል…፡፡
መልሶ ፎዚያ ጋ ደወለ ...አታነሳም ፤ በቤቱ ስልክ ሞከረ አይነሳም፡፡ለጊዜው ሀሳቡን ሰበሰበና ሚስቱ ወደ ተኛችበት ክፍል አመራ.. እንዴት እንደሆነች ለማየት፡፡
ፎዚያ እንቅልፍ እንዲወስዳት ብትመኝም ከመገላበጥ ውጭ ሊሳካላት አልቻለም፡፡ሰባት ሰዓት ላይ ሞባይሏ ጮኸ ...ሰሎሞን መስሏት ችላ ልትለው ነበር ፡፡በተጨናበሰ ዓይኗ አጨንቁራ ስታየው ግን የውጭ ስልክ ነው ..ተስፈንጥራ አነሳችው፡፡
‹‹ሄሎ ፎዚ፡፡››ሁሴን ነበር የደወለላት፡፡
‹‹ሄሎ ሁስን..እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ፡፡ የትንግርት ስልክ አይሰራም… እስቲ አገናኚኝ?››
ደነገጠች ምን ትበለው‹‹የለችም፡፡››
‹‹የት ሄደች?››
‹‹ለስራ..ማለቴ... ከኤልያስ ጋር ሀዋሳ፡፡›› ተንተባተበችበት፡፡
‹‹ፎዚ እኔ በደንብ አውቅሻለሁ፤አንቺ ውሸት አትችይበትም...የሆነውን ንገሪኝ?››
‹‹እውነቴን ነው ሀዋሳ ነው የሄደችው፡፡››
‹‹ታዲያ ስልኳን ለምን ዘጋች?››
አመለጣት‹‹ታስራ ነው››
<<ምን!?>>
‹‹አዎ..እኔም ግራ ገብቶኛል...የሆነች አንድ ሴት በጠርሙስ ፈንክታ ነው አሉ የታሰረችው፡፡››
‹‹የምን ሴት…? በምን ተጣልተው?››
‹‹በምን እንደተጣሉ እስከአሁን አልታወቀም፡፡››
‹‹ማነች ሴትዬዋ?››
‹‹አላወቅኳትም...በቅርብ ከአሜሪካ የመጣች ዲያስፖራ ነች አሉ፡፡የሆነ የእርዳታ ድርጅት ውስጥ እንደምትሰራም ሰምቼያለው፡፡››
‹‹ስሟ ማን ነው?››
‹‹ውይ ስሟን አላውቅም?››
‹‹በይ ከአስር ደቂቃ በኃላ ደውላለሁ.. አጣርተሸ ጠብቂኝ፡፡›› ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ እንዳለው በ11 ደኛው ደቂቃ ደወለ፡፡
‹‹እሺ ፎዚ ምን አገኘሽ?››
‹‹ዶ/ር ሶፊያ ይድነቃቸው ትባላለች፡፡››መረጃውን ከኤልያስ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹ዶክተር ሶፊያ!!!?››
ይበልጥ አርበተበታት‹‹ አዎ ዶ/ር ሶፊያ… ምነው ታውቃታለህ?››
‹‹አዎ... ትንግርት ስለእሷ ነግራኛለች፡፡››
‹‹የት ነው የሚተዋወቁት?››
‹‹በጣም የሚዋደዱ ጓደኛሞች ነበሩ››አለ ፃረሞት ባረበበበት የሰለለ ድምፅ፡፡
ፎዚያ ከድንጋጤው የተነሳ መቃዠት የጀመረች መሰላት ‹‹ዶ/ር ሶፊያ እኮ ነው ያልኩህ ...፤የምን......................
‹‹ተይው ፎዚ፤ ከባድ አደጋ ላይ ነን ያለነው፤በቃ ቻው ነገ እደውልልሻለሁ›› ብሎ ስልኩን አቆረጠው፡፡
ፎዚያም እንደፈዘዘች ከድምፅ አልባው ሞባይሏ ጋር ተፋጣ ቀረች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ 5 ሰው #subscribe ካደረገ ቀጣዩ ክፍል ማታ 3 ሰአት ላይ ይለቀቃል ዛሬ ከተሳካ እሞክራለው !!
#Share and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍107❤12🤔6👎2👏1😁1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
የተንታራሰችው ትራስ የሌላ ሰው ጠረን ይዞል…ደስ የሚል ተፈጥሯዊ ጠረን…እዚህ አልጋ ላይ አብሯት የተኛ ወንድ ፋሲል ብቻ ነበር ፤እሱንም ጨክና አስገድለዋለች….ትናንት ሌላ ወንድ በራሱ ፍቃድ ሰተት ብሎ ገብቶ ከጎኗ በመተኛት አስደምሟታል፡፡ማስደመም ብቻም ሳይሆን ልቧንም ሸርሽሮባታል… ሚኒዬነሩ ዘበኛዋ….ታሪኩ ራሱ ህልም ነው የሆነባት….ስለእሱ እያሰበች የመኝታ ቤቷ በራፉ ተከፈተ …አለምን ነበር የጠበቀችው….ወደውስጥ እየገባ የነበረው ግን ቀናው ነበር…የሼፎችን አይነት አለባበስ ለብሷል…በእጁ ላይ ባለ ሰፋ ያለ ትሪ ላይ ትናንሽ ሳህኖች ተደርድረው በዛ ያሉ ምግቦችን ይዘዋል፡፡
ምግቡን መኝታ ቤት የምትገኘው አነስተኛ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠና መኝታ ክፍል ውስጥ ወዳለ አነስተኛ ፍርጂ በመሄድ ውሀ አወጣ… አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ…ከዛ ከምግቡ ጠቀለለና በተኛችበት ወደአፏ አስጠጋላት… በጣም ከመደንገጧና ከመደመሟ የተነሳ ያለምንም ተቃውሞ አፏን በጠባቡም ቢሆን ከፈተች…አጎረሳት…፡፡እንደምንም አላምጣ ስትወጥ እየጠበቀ ያጎርሳታል.. በመሀከል ለራሱም አንድ ሁለቴ ይጎርሳል… እደምንም ብላ አንድ ስምንት የሚሆን ጉርሻ ጎረሰችና ከአቅሟ በላይ ሲሆንባት በቃኝ አለችው፡፡
ያ ምግብ ትብለጥን ወደ ወህኒ ልካ በክፍሏ ከተከተተች በባለፈው ሁለት ወር ውስጥ ወደሆዷ የገባ ብዛት ያለው ምግብ ነው። እሱም ለራሱ የተወሰነ ከጎራረሰ በኃላ ምግብ የተቀመጠበትን ጠረጴዛ ከአልጋው ራቅ አድርጎ አስቀመጠና የታሸገ ውሀውን በማንሳት ክዳኑን ከፈተና አቀበላት። ከትራሷ በመጠኑ ቀና ብላ የተወሰነ ጠጣችለትና መልሳ ሰጠችው።
"ሌላ የምትፈልጊው ነገር ከሌለ መሄዴ ነው? "አላት። "እስኪ ቁጭ በል"አለችው።
ጥያቄዋን ተቀብሎ ከአልጋው ጠርዝ ላይ መልሶ ተቀመጠ"ደህና ነህ አይደል..? ማለቴ ትናንት ህመምህን ለእኔ ስትል ..."
"አታስቢ ሰላም ነኝ"
"ጥሩ..ጥያቄ ብጠይቅህ ቅርይልሀል?"
"የፈለግሽውን"
" ካምፓኒው ማለቴ የባለቤትህ ነበር..አሁን ማን ወረሰው?"
"ማንም ..አሁንም የእኔ ንብረት ነው..አሁንም በጥሩ ሁኔታ እየሠራ ነው..የእሷ ስም የያዘ ካምፓኒ በመሆኑ የበለጠ እንዲያድግ ነው የምፈልገው.."
"እና የአንተ በቅርብ አለመኖርህ ችግር አይፈጥርም"
"በፍፅም… ያ ካምፓኒ ከቤተሰብ ሲዎረስ የመጣና ከ80 ዓመት በላይ እድሜ ያለው ነው..እዛ ደግሞ እንደእኛ ሀገር አይደለም ..ነገሮች በህግና በስርዓት ስለሚመሩ በተለይ የደረጀ ድርጅት ባለቤቱ ቢኖርም ባይኖርም ልዩነቱ ያን ያህል ነው።ደግሞም እንደእቅዴ ከዛሬ 15 ቀን በፊት ተመልሼ ስራዬ ላይ የመሆን እቅድ ነበረኝ››
‹‹እና ታዲያ ለምን ሳትሄድ…?ደግሞስ እንደዛ ሚኒዬነር ሆነህ እዚህ ዘበኝነት ለምን ?አልገባኝም።››
‹‹እኔም አልገባኝም..በነገራችን ላይ እስከአሁን የካምፓኒው ወስጄ የተጠቀምኩት ብር የለም… እንደዛ ለማድረግ እቅድ የለኝም..እኔም የራሴ የሆነ የተወሰነ ብር አለኝ።ትናንት እንደነገርኩሽ እዚህ የመጣሁት ለስድስት ወር ነበር… እንደመጣሁ ለሁለት ወር ሆቴል ነበር ያረፍኩት.. ግን ሰለቸኝ። አፓርታማ ተከራይቼ ልወጣ አስብኩና ድንገት የእብደት የሚመስል ሀሳብ መጣብኝ።..ለምን መልሼ እንደድሀ አልኖርም..ምን አልባት ያ ሁሉ ቅጣት የመጣብኝ የማይገባኝ የድሎት ቆጥ ላይ ስለተንጠለጠልኩ ይሆናል ..እስኪ ለትንሽ ወራትም ቢሆን ድህነትን መልሼ ላጣጥመው ብዬ አሰብኩና ከክፍለ ሀገር ስራ ፍለጋ እንደመጣሁ ተናግሬ ቄራ አካባቢ አንድ ክፍል ቤት ተከራይቼ ገባሁ።እና በሰላም አንድ ወር ያህል እንደኖርኩ ከጎኔ ተከራይቶ የሚኖር አንድ ደላላ ነበር ሲገባ ሲወጣ ሰላም መባባል ጀመርን… ተግባባን በወሬ በወሬ ስራ አጥ መሆኔን ነገርኩት። እንደዛ የነገርኩት ስራ እንዲፈልግልኝ አልነበረም።እሱ ግን ዘበኝነት ካላስቀጠርኩህ..አሪፍ ቤት ነው ሴተ-ላጤ ነች..ካልተመቸህ ወዲያው ትለቃለህ ብሎ ድርቅ አለብኝ።ወደአሜሪካ ለመመለስ ከሶስት ወር ያነሰ ጊዜ ቢቀረኝም እንደአድቨንቸር ለምን አልወስደውም አልኩና እሺ አልኩት፡፡ አመጣና ካንቺ ጋር አስተዋወቀኝ..ስራ ጀመርኩ ..ይሄው አራተኛ ወር ልደፍን ነው።
ፈገግ አለችና ‹‹እና እንዴት ነው ስራው ተመቸህ?"ስትል ጠየቀችው፡፡
"አዎ..በጣም እንጂ ...ከመልመዴና ከመደላደሌ የተነሳ የራሴ ቤት ሁሉ እየመሠለኝ ተቸግሬለሁ።››
ዝም አለች‹‹...አመሠግናለሁ..እንዲህ እንዳወራ ስላደረከኝ አመሠግናለሁ።››
"አንቺም ዳግመኛ ለሌላ ሰው መጨነቅ እንድጀምርና ...አሁንም እስትንፋሴ ያልተቋረጠ ሰው እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ስላደረግሺኝ በጣም አመሠግናለሁ"
‹እና አሜሪካ መሄዱንስ?›
‹‹በሁለት ወር አራዘምኩት››
‹‹ለምን እንደሆነ መጠየቅ እችላለሁ?››
‹‹ሳይሽ ባለፉት አመታት ያሳለፍኩትን መከራ ነው የምታስታውሺኝ..እንደዚህ ሆነሽ ብሄድ የሆነ ግማሽ ማንነቴን እዚሁ አንቺ መኝታ ቤት ቆልፌበት እንደሄድኩ ነው የምቆጥረው..እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሄጄም ሰላም ማገኝ አይመስለኝም››
‹‹እና መቼም ከዚህ ካልተነሳሁስ?ምን ልታደርግ ነው?››
‹‹ሳባ በዚህች ሶስት ወር ስላንቺ እንደተረዳሁት አንቺ ደጋ ላይ በቅላ ያደገች ..ግን ንፋስ ድንገት አንገዋሎ በረሀ መሀከል የጣላት ...ያንንም መልመድና መቀበል አቅቷት የደነገጠች የፅጌረዳ አበባ ነሽ...ያቺ አበባ ባለመደችው የውሀ ጥም ጉሮሮዋ ተሰነጣጥቆ እየሟሸሸች ነው። ...ያቺን ማራኪ ፅጌረዳ አበባ በፀሀይ ንዳድ ስትነድ የህይወት ፈሳሿ ከውስጧ ተሟጦ ሲያልቅ እያየሁ በከፍተኛ ትዕግስት እና በጥልቅ ሀዘን ስታዘብ ቆይቼያለሁ።ማየት ብቻም ሳይሆን ምን አልባት ላድናት እችል ይሆን ?በሚል ተስፋ ዙሪያዋን በመኮትኮት በኮዳዬ ለክፍ ቀን ብዬ ያኖርኩትን የውሀ ጠብታ በስሯ ዙሪያ ለማንጠባጠብ በጥቂቱም ቢሆን እየሞከርኩ ነው ፡፡ስሯ ግን በራሱ ሀዘን ጨልሞ መምጠጫ ቀዳዳውን ፅልመት ስለደፈነበት የዕንቁ ያህል ዋጋ ያላቸው ህይወት አድን የውሀ ጠብታዋቼን በከንቱ የበረሀው ንዳድ በላቸው።እና እኔ ከንቱው ከዚህ በላይ እዚህ ቆይቼ የፅጌረዳዋ ቅጠሎች ከመወየብና ከመጠውለግ አልፈው እስኪረግፋ ማየት አልችልም፡፡ደግሞ በቅጠል መርገፍ ብቻ የሚያበቃ መስሎ አልታየኝም...የግንድ መሞሸሽና ሙሉ በሙሉ መፍረስ ሊያጋጥም ይችላል...እኔ ታዲያ በየትኛው ብረት ልቤ ይሄንን እስከፍፃሜው ጠብቄ ማየት እችላለሁ..አይ እኔ ለዛ የተሰራሁ አይነት ሰው አይደለሁም..
እና ለእኔ ስትይ ይህቺን ፅጌረዳ አድኚያት ...ወይ የሚበቃትን ያህል የህይወት ውሀ ያለችበት በረሀ ድረስ በመውሰድ ስሯ እስኪረሰርስ፤ሙሽሽ ብሎ የተኛው ቅጠሏ እስኪነቃና እስኪቃና አጠጪያት… ወይ ደግሞ ቀስ ብለሽ ስሯን ሳትነኪ ዙሪያዋን በመቋፈር ከነስሯ ንቀያትና ቀድሞ ወደበቀለችበትና ወዳደገችበት ስፍራ... ወደለመደችውና ወደምትናፍቀው ቀሄ በመውሰድ መልሰሽ ትከያት።...ለዛ 15 ቀን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
የተንታራሰችው ትራስ የሌላ ሰው ጠረን ይዞል…ደስ የሚል ተፈጥሯዊ ጠረን…እዚህ አልጋ ላይ አብሯት የተኛ ወንድ ፋሲል ብቻ ነበር ፤እሱንም ጨክና አስገድለዋለች….ትናንት ሌላ ወንድ በራሱ ፍቃድ ሰተት ብሎ ገብቶ ከጎኗ በመተኛት አስደምሟታል፡፡ማስደመም ብቻም ሳይሆን ልቧንም ሸርሽሮባታል… ሚኒዬነሩ ዘበኛዋ….ታሪኩ ራሱ ህልም ነው የሆነባት….ስለእሱ እያሰበች የመኝታ ቤቷ በራፉ ተከፈተ …አለምን ነበር የጠበቀችው….ወደውስጥ እየገባ የነበረው ግን ቀናው ነበር…የሼፎችን አይነት አለባበስ ለብሷል…በእጁ ላይ ባለ ሰፋ ያለ ትሪ ላይ ትናንሽ ሳህኖች ተደርድረው በዛ ያሉ ምግቦችን ይዘዋል፡፡
ምግቡን መኝታ ቤት የምትገኘው አነስተኛ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠና መኝታ ክፍል ውስጥ ወዳለ አነስተኛ ፍርጂ በመሄድ ውሀ አወጣ… አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ…ከዛ ከምግቡ ጠቀለለና በተኛችበት ወደአፏ አስጠጋላት… በጣም ከመደንገጧና ከመደመሟ የተነሳ ያለምንም ተቃውሞ አፏን በጠባቡም ቢሆን ከፈተች…አጎረሳት…፡፡እንደምንም አላምጣ ስትወጥ እየጠበቀ ያጎርሳታል.. በመሀከል ለራሱም አንድ ሁለቴ ይጎርሳል… እደምንም ብላ አንድ ስምንት የሚሆን ጉርሻ ጎረሰችና ከአቅሟ በላይ ሲሆንባት በቃኝ አለችው፡፡
ያ ምግብ ትብለጥን ወደ ወህኒ ልካ በክፍሏ ከተከተተች በባለፈው ሁለት ወር ውስጥ ወደሆዷ የገባ ብዛት ያለው ምግብ ነው። እሱም ለራሱ የተወሰነ ከጎራረሰ በኃላ ምግብ የተቀመጠበትን ጠረጴዛ ከአልጋው ራቅ አድርጎ አስቀመጠና የታሸገ ውሀውን በማንሳት ክዳኑን ከፈተና አቀበላት። ከትራሷ በመጠኑ ቀና ብላ የተወሰነ ጠጣችለትና መልሳ ሰጠችው።
"ሌላ የምትፈልጊው ነገር ከሌለ መሄዴ ነው? "አላት። "እስኪ ቁጭ በል"አለችው።
ጥያቄዋን ተቀብሎ ከአልጋው ጠርዝ ላይ መልሶ ተቀመጠ"ደህና ነህ አይደል..? ማለቴ ትናንት ህመምህን ለእኔ ስትል ..."
"አታስቢ ሰላም ነኝ"
"ጥሩ..ጥያቄ ብጠይቅህ ቅርይልሀል?"
"የፈለግሽውን"
" ካምፓኒው ማለቴ የባለቤትህ ነበር..አሁን ማን ወረሰው?"
"ማንም ..አሁንም የእኔ ንብረት ነው..አሁንም በጥሩ ሁኔታ እየሠራ ነው..የእሷ ስም የያዘ ካምፓኒ በመሆኑ የበለጠ እንዲያድግ ነው የምፈልገው.."
"እና የአንተ በቅርብ አለመኖርህ ችግር አይፈጥርም"
"በፍፅም… ያ ካምፓኒ ከቤተሰብ ሲዎረስ የመጣና ከ80 ዓመት በላይ እድሜ ያለው ነው..እዛ ደግሞ እንደእኛ ሀገር አይደለም ..ነገሮች በህግና በስርዓት ስለሚመሩ በተለይ የደረጀ ድርጅት ባለቤቱ ቢኖርም ባይኖርም ልዩነቱ ያን ያህል ነው።ደግሞም እንደእቅዴ ከዛሬ 15 ቀን በፊት ተመልሼ ስራዬ ላይ የመሆን እቅድ ነበረኝ››
‹‹እና ታዲያ ለምን ሳትሄድ…?ደግሞስ እንደዛ ሚኒዬነር ሆነህ እዚህ ዘበኝነት ለምን ?አልገባኝም።››
‹‹እኔም አልገባኝም..በነገራችን ላይ እስከአሁን የካምፓኒው ወስጄ የተጠቀምኩት ብር የለም… እንደዛ ለማድረግ እቅድ የለኝም..እኔም የራሴ የሆነ የተወሰነ ብር አለኝ።ትናንት እንደነገርኩሽ እዚህ የመጣሁት ለስድስት ወር ነበር… እንደመጣሁ ለሁለት ወር ሆቴል ነበር ያረፍኩት.. ግን ሰለቸኝ። አፓርታማ ተከራይቼ ልወጣ አስብኩና ድንገት የእብደት የሚመስል ሀሳብ መጣብኝ።..ለምን መልሼ እንደድሀ አልኖርም..ምን አልባት ያ ሁሉ ቅጣት የመጣብኝ የማይገባኝ የድሎት ቆጥ ላይ ስለተንጠለጠልኩ ይሆናል ..እስኪ ለትንሽ ወራትም ቢሆን ድህነትን መልሼ ላጣጥመው ብዬ አሰብኩና ከክፍለ ሀገር ስራ ፍለጋ እንደመጣሁ ተናግሬ ቄራ አካባቢ አንድ ክፍል ቤት ተከራይቼ ገባሁ።እና በሰላም አንድ ወር ያህል እንደኖርኩ ከጎኔ ተከራይቶ የሚኖር አንድ ደላላ ነበር ሲገባ ሲወጣ ሰላም መባባል ጀመርን… ተግባባን በወሬ በወሬ ስራ አጥ መሆኔን ነገርኩት። እንደዛ የነገርኩት ስራ እንዲፈልግልኝ አልነበረም።እሱ ግን ዘበኝነት ካላስቀጠርኩህ..አሪፍ ቤት ነው ሴተ-ላጤ ነች..ካልተመቸህ ወዲያው ትለቃለህ ብሎ ድርቅ አለብኝ።ወደአሜሪካ ለመመለስ ከሶስት ወር ያነሰ ጊዜ ቢቀረኝም እንደአድቨንቸር ለምን አልወስደውም አልኩና እሺ አልኩት፡፡ አመጣና ካንቺ ጋር አስተዋወቀኝ..ስራ ጀመርኩ ..ይሄው አራተኛ ወር ልደፍን ነው።
ፈገግ አለችና ‹‹እና እንዴት ነው ስራው ተመቸህ?"ስትል ጠየቀችው፡፡
"አዎ..በጣም እንጂ ...ከመልመዴና ከመደላደሌ የተነሳ የራሴ ቤት ሁሉ እየመሠለኝ ተቸግሬለሁ።››
ዝም አለች‹‹...አመሠግናለሁ..እንዲህ እንዳወራ ስላደረከኝ አመሠግናለሁ።››
"አንቺም ዳግመኛ ለሌላ ሰው መጨነቅ እንድጀምርና ...አሁንም እስትንፋሴ ያልተቋረጠ ሰው እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ስላደረግሺኝ በጣም አመሠግናለሁ"
‹እና አሜሪካ መሄዱንስ?›
‹‹በሁለት ወር አራዘምኩት››
‹‹ለምን እንደሆነ መጠየቅ እችላለሁ?››
‹‹ሳይሽ ባለፉት አመታት ያሳለፍኩትን መከራ ነው የምታስታውሺኝ..እንደዚህ ሆነሽ ብሄድ የሆነ ግማሽ ማንነቴን እዚሁ አንቺ መኝታ ቤት ቆልፌበት እንደሄድኩ ነው የምቆጥረው..እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሄጄም ሰላም ማገኝ አይመስለኝም››
‹‹እና መቼም ከዚህ ካልተነሳሁስ?ምን ልታደርግ ነው?››
‹‹ሳባ በዚህች ሶስት ወር ስላንቺ እንደተረዳሁት አንቺ ደጋ ላይ በቅላ ያደገች ..ግን ንፋስ ድንገት አንገዋሎ በረሀ መሀከል የጣላት ...ያንንም መልመድና መቀበል አቅቷት የደነገጠች የፅጌረዳ አበባ ነሽ...ያቺ አበባ ባለመደችው የውሀ ጥም ጉሮሮዋ ተሰነጣጥቆ እየሟሸሸች ነው። ...ያቺን ማራኪ ፅጌረዳ አበባ በፀሀይ ንዳድ ስትነድ የህይወት ፈሳሿ ከውስጧ ተሟጦ ሲያልቅ እያየሁ በከፍተኛ ትዕግስት እና በጥልቅ ሀዘን ስታዘብ ቆይቼያለሁ።ማየት ብቻም ሳይሆን ምን አልባት ላድናት እችል ይሆን ?በሚል ተስፋ ዙሪያዋን በመኮትኮት በኮዳዬ ለክፍ ቀን ብዬ ያኖርኩትን የውሀ ጠብታ በስሯ ዙሪያ ለማንጠባጠብ በጥቂቱም ቢሆን እየሞከርኩ ነው ፡፡ስሯ ግን በራሱ ሀዘን ጨልሞ መምጠጫ ቀዳዳውን ፅልመት ስለደፈነበት የዕንቁ ያህል ዋጋ ያላቸው ህይወት አድን የውሀ ጠብታዋቼን በከንቱ የበረሀው ንዳድ በላቸው።እና እኔ ከንቱው ከዚህ በላይ እዚህ ቆይቼ የፅጌረዳዋ ቅጠሎች ከመወየብና ከመጠውለግ አልፈው እስኪረግፋ ማየት አልችልም፡፡ደግሞ በቅጠል መርገፍ ብቻ የሚያበቃ መስሎ አልታየኝም...የግንድ መሞሸሽና ሙሉ በሙሉ መፍረስ ሊያጋጥም ይችላል...እኔ ታዲያ በየትኛው ብረት ልቤ ይሄንን እስከፍፃሜው ጠብቄ ማየት እችላለሁ..አይ እኔ ለዛ የተሰራሁ አይነት ሰው አይደለሁም..
እና ለእኔ ስትይ ይህቺን ፅጌረዳ አድኚያት ...ወይ የሚበቃትን ያህል የህይወት ውሀ ያለችበት በረሀ ድረስ በመውሰድ ስሯ እስኪረሰርስ፤ሙሽሽ ብሎ የተኛው ቅጠሏ እስኪነቃና እስኪቃና አጠጪያት… ወይ ደግሞ ቀስ ብለሽ ስሯን ሳትነኪ ዙሪያዋን በመቋፈር ከነስሯ ንቀያትና ቀድሞ ወደበቀለችበትና ወዳደገችበት ስፍራ... ወደለመደችውና ወደምትናፍቀው ቀሄ በመውሰድ መልሰሽ ትከያት።...ለዛ 15 ቀን
👍82❤11👏2🥰1😁1
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
===================
የሰሎሜ ህክምናው በሰላም ተጠናቆ ወደ ቤት ተመልሳለች፡፡እናትዬው ብቻ ሳትሆን ሁሴን እና አለማየሁም ከስሯ ሳይለዩ ልክ ልጅ ሆነው ታማ ሆስፒታል በገባች ጊዜ እንዳደረጉት በትኩረትና በሙሉ ጥረት ሲንከባበከቦት ነበር የከረሙት፡፡በዛ ምክንያት የማገገም ፍጥነቷ ተአምር የሚባል ነበር፡፡
አሁን ሁለቱ ጓደኛሞች አለማየሁ እና ሁሴን በዛሬው ቀን ከውጭ የሚመጣውን ጓደኛቸውን ሊቀበሉ ቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡አላዛር ሰሎሜ ለመቅኔ ንቅለ ተከላ የሚያደርስ ህመም ታማ እንደነበረ አልሰማም፡፡ ኬሞትራፒ እክምና ላይ እያለች ይሁን ከዛ ወጥታ ኮማ ውስጥ ገብታ ሳለ በስልክ እንድታናግረው በሚጠይቅበት ጊዜ ኃይለኛ ጉንፋን ይዟት ድምፆ ተዘግቷል ብለው ሸውደውታል፡፡እንደዛ ያደረጉት የሄደበትን ጉዳይ ያለምንም እንቅፋት እንዲያጠናቅቅ ስለፈለጉ ነው፡፡ይሄ ውሳኔ የአለማየሁ ነው፡፡ሌሎቹንም ያሳመናቸው እሱ ነው፡፡
‹‹ተሳክቶለት የሚመጣ ይመስልሀል?››ሁሴን ነው ፈራ ተባ እያለ አለማየሁን የጠየቀው፡፡
‹‹ይመስለኛል..በስልክ ሳወራው እሱም ሙሉ በሙሉ እንደዳነ እርግጠኛ ነው››ሲል መለሰለት፡፡
‹‹ደስ ይላል ….እርግጠኛ ነኝ አሁን አንተም ሙሉ በሙሉ እንዲሳካለት ነው የምትፈልገው››በማለት የሚያስገርም ነገር ነገረው፡፡
‹‹ማለት ?››
‹‹ያው አሁን ወንድሟ መሆንህን አውቀሀል…ከትዳሯ መፍረስ ምንም ምታተርፈው ነገር የለም…እንደውም በተቃራኒው ታዝናለህ››
‹‹በፊትስ ቢሆን ምን አተርፍ ነበር?››
‹‹ባክህ ምን ያደባብቅሀል፡፡ እድሜ ልካችንን እኮ እርስ በርስ እንተዋወቃለን….ባይሳካለት ያንን ክፍተት ተጠቅመህ የሆነ ነገር ለማድረግ አሰፍስፈህ በመጠባበቅ ላይ ነበርክ….››ብሎ የሚያምንበትን ነገር ያለምንም ይኑኝታ ፍርጥ አድርጎ ተናገረ፡፡
አለማየሁም ያልገባው በመምሰል‹‹የሆነ ነገር ማለት?››ሲል ተጨማሪ ማብራሪያ ጠየቀው፡፡
‹‹ከአላዛር ልታፋታትና እራስህ ልታገባት…ተሳሳትኩ?ደግሞ ይሄንን አቋምህን ቀጥታ ለእሱም ነግረሀዋል…››
‹‹እሱ ነው እንደዛ ብሎ የነገረህ?››
‹‹ማን እንደነገረኝ ማወቁ ምን ያደርግልሀል..?ብቻ እንደዛ ለማድረግ እቅድ እንደነበረህ አውቃለው››
‹‹አሀ..አሁን አንተም እኔ ማድረግ አቅጄ እንደነበረው ለማድረግ እያሰብክ ነው ማለት ነው?››ሲል በገረሜታ ጠየቀው፡፡
‹‹መጀመሪያ ያንተን መልስልኝ››
‹‹አሁን እዚህ ጉዳይ ላይ ማውራት ምን ይረባል?››
‹‹በጣም ይረባል…አሁን አንተ ወንድሟ ስለሆንክ ስለእሷ ወደፊት መጨነቅና ማሰብህ የሚጠበቅብህ ሁኔታ ላይ ነው ያለኸው…ከአላዘር ጋር ካልተሳካላትና የሚፋቱ ከሆነ እኔን እንድታገባኝ ታግዘኛለህ…?.››
‹‹ይሄ ሁሉ ዙሪያ ጥምዝ ….ይሄን ለማለት ነው?››
‹‹አዎ…ታውቃለህ ልክ አንተ ታፈቅራት በነበረው መጠን አፈቅራታለው…እሷ ለሁላችንም የእድሜ ልክ ህልማችን ነች፡፡እሱ እድሉን ተጠቅሟል…ካልሆነለት ቀጣይ የእኔ እድል ነው፡፡እኔ ደግሞ በምንም አይነት ተአምር እድሌን ማባከን አልፈልግም…ቀሪ ዘመኗን እንደሳቀች እንድትኖር ነው የማደርጋት፡፡››
አለማየሁ ምን ሊመልስለት እንደሚገባ መወሰን አልቻለም..ዝም ብሎ ትካዜ ውስጥ ገባ….ሁሴን እየተናገረው ያለው ነገር ደረቅና የሚያሳቅቅ አይነት ቢሆንም ግን ደግሞ እሱም ወንድሟ መሆኑን ከማወቁ በፊት ለማድረግ ሲያስብ እና ሲመኘው የነበረ ነገር ነው አሁን እሱ እያወራ ያለው፡፡እሱ ሲያደርገው ትክክል ሌላ ሲያደርገው ደግሞ አፀያፊ የሚሆንበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ደግሞም ለእሱም ቢሆን የአላዛር ህክምና የማይሳካለት ከሆነ እህቱ ከዚህ በላይ ከእሱ ጋር እየተሰቃየችና እየተሳቀቀች እንድትቀጥል አይፈቅድም…ከአላዛር ከተለያየች ደግሞ ከሁሴን የተሻለ ሰው ታገኛለች ቡሎ አያስብም…ወደደም ጠላም በእሱ ሀሳብ ተስማምቶ ሊረዳው ግድ ነው፡፡
‹‹ጥሩ …ባልከው ነገር እስማማለሁ..፡፡በመጀመሪያ ግን የአላዛር ውጤት በግልፅ ከመታወቁ በፊት ምንም አይነት እንቅስቃሴ አታደርግም፡፡እሱ በግማሽ እንኳን ለውጥ አሳይቶ ከመጣ ሙሉ በሙሉ እንዲያገግም እንረዳዋለን እንጂ ተስፋውን ለማጨለም ምንም አይነት አሻጥር አንሰራም፡፡››
‹‹እስማማለሁ…ሰሎሜን አፈቅራታለሁ ስልህ እኮ የእውነት ነው የማፈቅራት…ደግሞ እሷን ብቻ ሳይሆን እሱንም በጣም የምወደው ወንድሜ ነው፡፡ የመጀመሪያ ምርጫዬ በመሀከላቸው ያለው ችግር ተቀርፎ ትዳራቸውን አጣፍጠው መኖር እንዲቀጥሉ ነው…..፡፡ትዳሩ እንደማይቀጥል እርግጠኛ እስክሆን ድርስ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አላደርግም..ለዛ ቃል ገባልሀለው፡፡››
‹‹ጥሩ ..ሌላው…ነገሮች የማይሆኑ ሆነው..እሷን የማግባቱ እድል ያንተ ከሆነ ከውጭ ጓዝህን ጠቅልለህ ትመጣለህ…ይዣት ልሂድ የምትል ከሆነ ..አልስማማም›
‹‹የእሷ ፍላጎት ከሀገር ውጭ ሄዶ መኖር ከሆነስ?››
‹‹ነገርኩ እኮ…ከአሁን በኃላ ከእህቴ ተለይቼ መኖር አልችልም…እዚሁ በቅርቤ እንድትሆን ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹.ጥሩ …ለእኔ ችግር የለውም ..እሷን እስከአገኘሁ ድረስ የትም ብኖር ደስተኛ ነኝ፡፡››
ስምምነታቸውን አገባደው ወደ ግል ትካዜያቸው ተመልሰው ገቡ..የአላዛርን መምጣት ሲያዩ ነበር ከትካዜያቸው ባነው የተንቀሳቀሱት፡፡የሞቀ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኃላ…ወደመኪና ይዘውት እየሄዱ ሳለ አላዛር ‹‹ሰሎሜስ…?አብራችሁ ትመጣለች ብዬ ነበር?››ሲል ቅሬታውን አሰማ፡፡
አለማየሁ ፈጠን አለና ‹‹አልቻለችም…አንተን በደመቀ ቤት ለመቀበል ሽር ጉድ እያለች ነው፡፡››የሚል የውሸት ምክንያት ነገረው፡
‹‹እኔን ለመቀበል የምን ሽርጉድ ያስፈልጋል…?አንድ ወር ብቻ እኮ ነው የቆየሁት››እያለ በመነጫነጭ መኪና ውስጥ ገባ፡፡በአለማየሁ ሹፌርነት ወደቤት ጉዞ ጀመሩ…፡፡
አላዛር እቤት ሲደርሱ ሰሎሜን አግኝቶ ናፍቆቱን ለመወጣት ባለው ጉጉት ቀጥታ ተንደርድሮ ወደሳሎን ነው የገባው ፡፡እቴቴና ሰራተኞቹ የምግብ ጠረጴዛው ላይ ምግብን ለመደርደር ሽር ጉድ እያሉ ነው… ሰሎሜን ማየት አልቻለም፡፡ውስጡን ፋራቻ ወረረው፡፡ ግን ወዲያው ሶፋው ላይ ጋቢ ለብሳ ተኝታ ተመለከታት፡፡ተንደረደረና ስሯ ደርሶ ተንበረከከ‹‹እንዴ የእኔ ፍቅር እስከዛሬ እያመመሽ ነው እንዴ?››ብሎ ተጠመጠመባት፡፡
‹‹ቀስ ቀስ…ሰውነቷ ገና በቅጡ አላገገመም››ሲሉ እናትዬው አስጠነቀቁት፡፡
‹‹ማለት››
‹‹የመቅኔ ንቅለተከላ ተደርጎላት ነበር..?››እናትዬው ነች ተናጋሪዋ
አላዛር ሚስቱን አፍጥጦ ተመለከታት፡፡ሰሎሜም ‹‹ትንሽ አሞኝ ነበር..››ስትል ጠቅላላ ሁኔታውን በአጭሩ አስረዳችው፡፡
‹‹ማለት ..?እንዴት ይሄ ሁሉ ሲሆን እኔ ሳልሰማ…?ለምን ልትደብቁኝ ፈለጋችሁ?የሆነ ነገር ሆናስ ቢሆን ?››ወደኃላ ዞሮ ጓደኞቹ ላይ አፈጠጠባቸው፡፡…ዘራፍ አለ ..ተንሰቅስቆ አለቀሰ..
‹‹ምንም አታስብ አሁን እኮ ሙሉ በሙሉ ድኜለሁ…እየን እስኪ በጣም እኮ ደህና ነኝ፡፡.ስራ ሁሉ እኮ መስራት እችላለው…እነእማዬ ትንሽ አገግሚ ስላሉኝ እኔም ትንሽ ልሞላቀቅ ብዬ ነው ተኝቼ የጠበቅኩህ፡፡››ስትል አፅናናችው፡፡ከብዙ ምክርና ተግሳፅ በኋላ እንደምንም ተረጋጋ፡፡ሁሉም በተደረደረው ምግብ ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡እየተሳሳቁና እየተጎራረሱ አሪፍ እራት በሉ፡፡ሁሉም ከምግብ ጠረጴዛው ወደ ሶፋው ተሸጋግረው በመደዳ በመቀመጥ ከሰሎሜ በስተቀር ሁሉም የሚፈልገውን መጠጥ እየተጎነጨ ለሌላ ዙር ጫወታ ዝጉጁ ሆኑ.፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
===================
የሰሎሜ ህክምናው በሰላም ተጠናቆ ወደ ቤት ተመልሳለች፡፡እናትዬው ብቻ ሳትሆን ሁሴን እና አለማየሁም ከስሯ ሳይለዩ ልክ ልጅ ሆነው ታማ ሆስፒታል በገባች ጊዜ እንዳደረጉት በትኩረትና በሙሉ ጥረት ሲንከባበከቦት ነበር የከረሙት፡፡በዛ ምክንያት የማገገም ፍጥነቷ ተአምር የሚባል ነበር፡፡
አሁን ሁለቱ ጓደኛሞች አለማየሁ እና ሁሴን በዛሬው ቀን ከውጭ የሚመጣውን ጓደኛቸውን ሊቀበሉ ቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡አላዛር ሰሎሜ ለመቅኔ ንቅለ ተከላ የሚያደርስ ህመም ታማ እንደነበረ አልሰማም፡፡ ኬሞትራፒ እክምና ላይ እያለች ይሁን ከዛ ወጥታ ኮማ ውስጥ ገብታ ሳለ በስልክ እንድታናግረው በሚጠይቅበት ጊዜ ኃይለኛ ጉንፋን ይዟት ድምፆ ተዘግቷል ብለው ሸውደውታል፡፡እንደዛ ያደረጉት የሄደበትን ጉዳይ ያለምንም እንቅፋት እንዲያጠናቅቅ ስለፈለጉ ነው፡፡ይሄ ውሳኔ የአለማየሁ ነው፡፡ሌሎቹንም ያሳመናቸው እሱ ነው፡፡
‹‹ተሳክቶለት የሚመጣ ይመስልሀል?››ሁሴን ነው ፈራ ተባ እያለ አለማየሁን የጠየቀው፡፡
‹‹ይመስለኛል..በስልክ ሳወራው እሱም ሙሉ በሙሉ እንደዳነ እርግጠኛ ነው››ሲል መለሰለት፡፡
‹‹ደስ ይላል ….እርግጠኛ ነኝ አሁን አንተም ሙሉ በሙሉ እንዲሳካለት ነው የምትፈልገው››በማለት የሚያስገርም ነገር ነገረው፡፡
‹‹ማለት ?››
‹‹ያው አሁን ወንድሟ መሆንህን አውቀሀል…ከትዳሯ መፍረስ ምንም ምታተርፈው ነገር የለም…እንደውም በተቃራኒው ታዝናለህ››
‹‹በፊትስ ቢሆን ምን አተርፍ ነበር?››
‹‹ባክህ ምን ያደባብቅሀል፡፡ እድሜ ልካችንን እኮ እርስ በርስ እንተዋወቃለን….ባይሳካለት ያንን ክፍተት ተጠቅመህ የሆነ ነገር ለማድረግ አሰፍስፈህ በመጠባበቅ ላይ ነበርክ….››ብሎ የሚያምንበትን ነገር ያለምንም ይኑኝታ ፍርጥ አድርጎ ተናገረ፡፡
አለማየሁም ያልገባው በመምሰል‹‹የሆነ ነገር ማለት?››ሲል ተጨማሪ ማብራሪያ ጠየቀው፡፡
‹‹ከአላዛር ልታፋታትና እራስህ ልታገባት…ተሳሳትኩ?ደግሞ ይሄንን አቋምህን ቀጥታ ለእሱም ነግረሀዋል…››
‹‹እሱ ነው እንደዛ ብሎ የነገረህ?››
‹‹ማን እንደነገረኝ ማወቁ ምን ያደርግልሀል..?ብቻ እንደዛ ለማድረግ እቅድ እንደነበረህ አውቃለው››
‹‹አሀ..አሁን አንተም እኔ ማድረግ አቅጄ እንደነበረው ለማድረግ እያሰብክ ነው ማለት ነው?››ሲል በገረሜታ ጠየቀው፡፡
‹‹መጀመሪያ ያንተን መልስልኝ››
‹‹አሁን እዚህ ጉዳይ ላይ ማውራት ምን ይረባል?››
‹‹በጣም ይረባል…አሁን አንተ ወንድሟ ስለሆንክ ስለእሷ ወደፊት መጨነቅና ማሰብህ የሚጠበቅብህ ሁኔታ ላይ ነው ያለኸው…ከአላዘር ጋር ካልተሳካላትና የሚፋቱ ከሆነ እኔን እንድታገባኝ ታግዘኛለህ…?.››
‹‹ይሄ ሁሉ ዙሪያ ጥምዝ ….ይሄን ለማለት ነው?››
‹‹አዎ…ታውቃለህ ልክ አንተ ታፈቅራት በነበረው መጠን አፈቅራታለው…እሷ ለሁላችንም የእድሜ ልክ ህልማችን ነች፡፡እሱ እድሉን ተጠቅሟል…ካልሆነለት ቀጣይ የእኔ እድል ነው፡፡እኔ ደግሞ በምንም አይነት ተአምር እድሌን ማባከን አልፈልግም…ቀሪ ዘመኗን እንደሳቀች እንድትኖር ነው የማደርጋት፡፡››
አለማየሁ ምን ሊመልስለት እንደሚገባ መወሰን አልቻለም..ዝም ብሎ ትካዜ ውስጥ ገባ….ሁሴን እየተናገረው ያለው ነገር ደረቅና የሚያሳቅቅ አይነት ቢሆንም ግን ደግሞ እሱም ወንድሟ መሆኑን ከማወቁ በፊት ለማድረግ ሲያስብ እና ሲመኘው የነበረ ነገር ነው አሁን እሱ እያወራ ያለው፡፡እሱ ሲያደርገው ትክክል ሌላ ሲያደርገው ደግሞ አፀያፊ የሚሆንበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ደግሞም ለእሱም ቢሆን የአላዛር ህክምና የማይሳካለት ከሆነ እህቱ ከዚህ በላይ ከእሱ ጋር እየተሰቃየችና እየተሳቀቀች እንድትቀጥል አይፈቅድም…ከአላዛር ከተለያየች ደግሞ ከሁሴን የተሻለ ሰው ታገኛለች ቡሎ አያስብም…ወደደም ጠላም በእሱ ሀሳብ ተስማምቶ ሊረዳው ግድ ነው፡፡
‹‹ጥሩ …ባልከው ነገር እስማማለሁ..፡፡በመጀመሪያ ግን የአላዛር ውጤት በግልፅ ከመታወቁ በፊት ምንም አይነት እንቅስቃሴ አታደርግም፡፡እሱ በግማሽ እንኳን ለውጥ አሳይቶ ከመጣ ሙሉ በሙሉ እንዲያገግም እንረዳዋለን እንጂ ተስፋውን ለማጨለም ምንም አይነት አሻጥር አንሰራም፡፡››
‹‹እስማማለሁ…ሰሎሜን አፈቅራታለሁ ስልህ እኮ የእውነት ነው የማፈቅራት…ደግሞ እሷን ብቻ ሳይሆን እሱንም በጣም የምወደው ወንድሜ ነው፡፡ የመጀመሪያ ምርጫዬ በመሀከላቸው ያለው ችግር ተቀርፎ ትዳራቸውን አጣፍጠው መኖር እንዲቀጥሉ ነው…..፡፡ትዳሩ እንደማይቀጥል እርግጠኛ እስክሆን ድርስ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አላደርግም..ለዛ ቃል ገባልሀለው፡፡››
‹‹ጥሩ ..ሌላው…ነገሮች የማይሆኑ ሆነው..እሷን የማግባቱ እድል ያንተ ከሆነ ከውጭ ጓዝህን ጠቅልለህ ትመጣለህ…ይዣት ልሂድ የምትል ከሆነ ..አልስማማም›
‹‹የእሷ ፍላጎት ከሀገር ውጭ ሄዶ መኖር ከሆነስ?››
‹‹ነገርኩ እኮ…ከአሁን በኃላ ከእህቴ ተለይቼ መኖር አልችልም…እዚሁ በቅርቤ እንድትሆን ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹.ጥሩ …ለእኔ ችግር የለውም ..እሷን እስከአገኘሁ ድረስ የትም ብኖር ደስተኛ ነኝ፡፡››
ስምምነታቸውን አገባደው ወደ ግል ትካዜያቸው ተመልሰው ገቡ..የአላዛርን መምጣት ሲያዩ ነበር ከትካዜያቸው ባነው የተንቀሳቀሱት፡፡የሞቀ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኃላ…ወደመኪና ይዘውት እየሄዱ ሳለ አላዛር ‹‹ሰሎሜስ…?አብራችሁ ትመጣለች ብዬ ነበር?››ሲል ቅሬታውን አሰማ፡፡
አለማየሁ ፈጠን አለና ‹‹አልቻለችም…አንተን በደመቀ ቤት ለመቀበል ሽር ጉድ እያለች ነው፡፡››የሚል የውሸት ምክንያት ነገረው፡
‹‹እኔን ለመቀበል የምን ሽርጉድ ያስፈልጋል…?አንድ ወር ብቻ እኮ ነው የቆየሁት››እያለ በመነጫነጭ መኪና ውስጥ ገባ፡፡በአለማየሁ ሹፌርነት ወደቤት ጉዞ ጀመሩ…፡፡
አላዛር እቤት ሲደርሱ ሰሎሜን አግኝቶ ናፍቆቱን ለመወጣት ባለው ጉጉት ቀጥታ ተንደርድሮ ወደሳሎን ነው የገባው ፡፡እቴቴና ሰራተኞቹ የምግብ ጠረጴዛው ላይ ምግብን ለመደርደር ሽር ጉድ እያሉ ነው… ሰሎሜን ማየት አልቻለም፡፡ውስጡን ፋራቻ ወረረው፡፡ ግን ወዲያው ሶፋው ላይ ጋቢ ለብሳ ተኝታ ተመለከታት፡፡ተንደረደረና ስሯ ደርሶ ተንበረከከ‹‹እንዴ የእኔ ፍቅር እስከዛሬ እያመመሽ ነው እንዴ?››ብሎ ተጠመጠመባት፡፡
‹‹ቀስ ቀስ…ሰውነቷ ገና በቅጡ አላገገመም››ሲሉ እናትዬው አስጠነቀቁት፡፡
‹‹ማለት››
‹‹የመቅኔ ንቅለተከላ ተደርጎላት ነበር..?››እናትዬው ነች ተናጋሪዋ
አላዛር ሚስቱን አፍጥጦ ተመለከታት፡፡ሰሎሜም ‹‹ትንሽ አሞኝ ነበር..››ስትል ጠቅላላ ሁኔታውን በአጭሩ አስረዳችው፡፡
‹‹ማለት ..?እንዴት ይሄ ሁሉ ሲሆን እኔ ሳልሰማ…?ለምን ልትደብቁኝ ፈለጋችሁ?የሆነ ነገር ሆናስ ቢሆን ?››ወደኃላ ዞሮ ጓደኞቹ ላይ አፈጠጠባቸው፡፡…ዘራፍ አለ ..ተንሰቅስቆ አለቀሰ..
‹‹ምንም አታስብ አሁን እኮ ሙሉ በሙሉ ድኜለሁ…እየን እስኪ በጣም እኮ ደህና ነኝ፡፡.ስራ ሁሉ እኮ መስራት እችላለው…እነእማዬ ትንሽ አገግሚ ስላሉኝ እኔም ትንሽ ልሞላቀቅ ብዬ ነው ተኝቼ የጠበቅኩህ፡፡››ስትል አፅናናችው፡፡ከብዙ ምክርና ተግሳፅ በኋላ እንደምንም ተረጋጋ፡፡ሁሉም በተደረደረው ምግብ ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡እየተሳሳቁና እየተጎራረሱ አሪፍ እራት በሉ፡፡ሁሉም ከምግብ ጠረጴዛው ወደ ሶፋው ተሸጋግረው በመደዳ በመቀመጥ ከሰሎሜ በስተቀር ሁሉም የሚፈልገውን መጠጥ እየተጎነጨ ለሌላ ዙር ጫወታ ዝጉጁ ሆኑ.፡፡
👍55❤4