#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ያች በየጊዜው የምትጠገነውና የማያዘልቅ የገንዘብ መፍጃ ዕድሳት
የሚደረግላት የጉልላት ቮልስዋገን እየተንገጫገጨች መንቆርሰሷ አልቀረም፡፡
አውላላ ሜዳ ላይ ታጋልጠኛለች በማለት ሆዱን ቅር ያለው ዕለት በታክሲና በእግሩ መሔድ ይቀናዋል። አንዳንድ ቀን ተገፍታም ይሁን በበርቺ በርቺ
ተንቀሳቅሳ መሽከርከሯ ስለማይቀር እየተንገራገጨችም ቢሆን ይነዳታል፡፡
መንገድ ላይ ቀጥ ባለች ቁጥር ደግሞ ከየትም ለቃቅሞ ያገዛቸውን ልዩ ልዩ
መፍቻዎች፣ የብረታ ብረት ቅባት ካጠገበ አሮጊ ከረጢት ውስጥ ይዘከዝክና
ለማጠባበቅ ወደ ሞተሯ ይገሠግሣል። ምን ያደርጋል ታዲያ! ያን ውስብስብና
ቁልፍልፍ የብረት ቁልል ሲያይ “አሁን ደግሞ የትኛው ይሆን? ምን ዐይነት
ፍርጃ ነው! » ይልና አንዱን መፍቻ ወርውሮ እንቺ ቅመሽ ይላታል። በዚያው
ደግሞ ሌላ ዕቃ ይቀለጠምና ከናካቴው እንደ አበያ በሬ ለጥ ትላለች፡፡
ከተማዉ ውስጥ ያሉት ሽቃዮች የተሰናከለች ተሽከርካሪ አነፍንፈው ማግኘት ይችሉ ይመስል ወዲያውኑ እንደ ጉንዳን ይከቧታል። እሺ ካለች አለች፡
አለበለዚያም በምንጭሯ አስጎትቶም ይሁን ከወደ ጅራቷ አስጠምዞ አንዱ ጋ
አስጠግቷት ይሔዳል። ለገፉለትም ሆነ ለሳቡለት ሰዎች ስለት እንዳለበት ሰው
የሚሰጠውን ሰጥቶና ኣንጀቱን አሳርሮ በእግሩ ሲንገላወድ የነቀሉት ጭሰኛ
ይመስላል፡፡
እንድ ሰሞን ጥርሱን ነክሶ ስላሳደሳት የመኪና ወጉ ደርሷት ደኅና ስትሽከረከር ሰነበተች። እሱም ሠጋር በቅሉ ላይ እንደ ተቀመጠ የዱሮ መኳንንት ውስጧ ገብቶ ጉብ ይላል፡፡ የወዲያነሽ ጋር ሽርሽር ለመሔድ አስበን ስለ ነበር መኪናውን እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፡፡ 'ውሰድ አለ ቃሉን
ሠፈር አድርጎ በደኅንነቷ እየተመካ፡፡ «በዚህ ሰሞን ውቃቢ ቀርቧታል፡፡
እንዳጋጣሚ ግን በመሏ መጥቶ እንዱ ጋ ቀጥ ብላ ጉድ ካደረገችህ የራስህ
ጉዳይ ነው የለሁበትም!» ብሉኝ ቅዳሜ ማታ ወሰድኳት።
እኔና የወዲያነሽ ከንጋቱ አስራ አንድ ሰዓት እንደሆነ ለሁለታችን የሚበቃ ጥቂት ለስላሳ መጠጥና ምግብ ጭነን ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ጎጃም መንገድ ሰማንያ አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ተጓዝንባት፡፡ ምንም እንከንና ጉድለት ሳያጋጥመን ካሰብነው ቦታ እስክንደርስ ድረስ መኪናይቱን እያቆምኩ ባሻገር የሚታዩትን ተራሮችና ኮረብቶች ለጥ ያሉ ለምለም ሜዳዎችና የሽልጥልጥ ሸንተራራማ ገደሉች እያየን፡፡ ምቹ ቦታና መዝናኛ ነው ብዬ ከገመትኩት ሥፍራ ላይ እንደ ደረስኩ የመንገዱን ዳር አስይዤ አቆምኳት፡፡ያ ብዙ ቦታ ላይ በንዝረት የሚገጫገጨው ልል የብረታ ብረት ክፍል ጊዜያዊ ጸጥታ አገኘ። የመኪናይቱ ሙቀት ቀስ በቀስ ቀነሰ። የውስጧ ሞቃት አየር
በመስኮት በኩል በሚገባው ቀዝቃዛ አየር የተገፋ ቦታ ይለቃል፡፡ የመኪናይቱ
ፊት ወደ ሰሜን በመዞሩ በስተምሥራቅ በኩል ባለው መስኮት በከፍተኛ
ፍጥነት እየተግለበለበ የሚገባው አየር በትይዩው መስኮት እየተዥጎደጎደ
ይፈተለካል። የመኪናይቱ መሪ በስተግራ በኩል በመሆኑ የወዲያነሽን እየዳበሰ
የሚመጣው አየር ከላይዋ ላይ የለሰለሰ የሽቶ መዓዛ ያመጣና አወድወድ አድርጎኝ ይከተለባል። ባለፈው አየር እግር የሚተካው አየር ይክሰኛል። በእኔ በኩል ያለውን በር ከፍቼ እግሬን ወደ ውጪ ዘርግቼ ራሴን በየወዲያነሽ ጭን
ላይ አሳረፍኩት፡፡ አንጋጥጬ ስመለከታት አዘቅዝቃ አየችኝ፡፡ አዝራሮቼ በተከፈቱበት በኩል ቀኝ እጅዋን አሾልካ ደረቴን ስትደባብሰኝ የፍቅራዊ ደስታ ሰመመን አጥለቀለቀኝ፡፡ ጋደም እንዳልኩ ዐይኖቼ ተንገረገቡ፡፡ ዐሥራ አምስት ደቂቃ ያህል ቀ-ም እንዳደረግሁ ወደ ከተማ በሚያዘግም የጭነት መኪና ድምፅ ባንኜ ነቃሁ፡፡ ጥቂት ምዕራፎች ወደፊት ነዳሁ።
እንደገና ከመንገድ ገለል አድርጌ አቆምኳት። ሠላሳ ርምጃዎች ያህል
ወጣ ብዬ ስለ ነበር አንዳንድ አጫጭር ቁጥቋጦዎች በመኪናይቱ ተቀለጣጠሙ ጎማው የተሽከረከረባቸው በዚያው ሲቀሩ በመኪናይቱ ሆድ የተለመሰሉት ግን በመጠኑ ጎበጥበጥ ብለው ቀኑ፡፡ ከፊት ለፊታችን ጥቅጥቅ ያለ አጋምና ብሳና ድግጣና ምሥርች ዐልፎ ዐልፎ ኮርች በቅሉ አካባቢውን አይደፈር መሳይ ግርማ አልብሶታል። ወደ ዱሩ የምታስኬደው ቀጭን መንገድ ባረንጓዴ ወረቀት ላይ የተሰመረች ግራጫ መስመር ትመስላለች፡፡በዚቹ መንገድ በኩል ይዣት ልግባ ይሆን ይቅርብኝ እያልኩ ሳመነታ'
ስፈራና ስጠራጠር ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡
አንድ ውሳኔ ለመወሰን ጫካውን አፍጥጬ ስመለከት ጥቂት ራቅ
ብሎ አንድ አፈርቻና ሦስት አራት ያህል ዝንጉርጉር እንስሳት ከጫካው ውስጥ ተከታትለው ብቅ አሉ፡፡
ለጊዜው ልብ ብዬ ባለማየቴ ደንገጥ አልኩና «ምንድናቸው?» አልኩ።
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል ያደረገችው የወዲያነሽ «ፍየሉች ናቸው» አለችኝ፡፡
«እኔስ ሌላ ነገር መስለውኝ» ብዩ ነገሩን ወዲያ ወዲህ እምታታሁ፡፡ ደግነቱ
ስሜቴን ስላላወቀችብኝ ዝም አለች። ጥሎ አይጥሌ ሲረዳኝ አንድ እረኛ ብዙ
ፍየሎች እያንጋጋ ከጫካው ውስጥ ብቅ አለ፡፡ ከመኪና ወጥተን የየወዲያነሽን
እጅ ያዝ አድርጌ እንደቆምኩ እረኛው አጠገባችን ደረሰ። ደረቱ ላይ ሰፋ-ሰፋ
ያለ ኪሶች ያለባት የአቡጀዲ እጀ ጠባብ ለብሷል። የሁለቱም ኪሶቹ አፍ አደፍደፍ ብሎ ጠቁሯል። ሁለት ፍየሎች ተነጥለው ወደ ሌላ አቅጣጫ ስለሄዱ እነሱን ለመመለስ ነይ እሪያ!» ብሎ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ልብሱ ከበስተኋላው ቂጡ ላይ ድልህ የነካው ጋቢ መስሏል።
ከጉልበቱ በታች ያለው ሙጭርጭር በደረቀ ጭራሮ የተጠረገ የረገጥ ቤት መስሏል፡፡ በግራ ብብቱ ቀጠን ያለች ብትር አጣብቆ ይዟል። ዋሽንቱን በእጁ ውስጥ እያንከባለለ ያሻሻታል። ፍየሎቹ እየቀነጣጠቡ በአጠገባችን አለፉ፡፡ እረኛውም ከኋላ ከኋላቸው ከተፍ አለ። ልብሱ ላይ ዐልፎ ዐልፎ ጨጎጊት ተጣብቋል። አጋም ሲቃቅምበት የዋለው ከንፈሩ ጠቋቀሯል። እንኩታ ሲቸችግ የዋለ መስሏል።
ለስለስ ባለ ድምፅ "አንተ ልጅ ና እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ አልኩት፡፡ ነባር ፍርሃት ሳይሆን የጥርጣሬ ፍርሃት በፊቱ ላይ እየታየ በዝግታ መጥቶ ቆመ ወደ ጫካው እያመላከትኩት በዚ ጫካ ውስጥ መንገድ አለ እንዴ?ብዬ ጠየኩት? 'አዎ' ብሎ ባጭሩ መለሰልኝ፡፡
«እንግዲያውማ እዚ ቅርቡ መናፈስ ይቻላል፣ አስቸገሩኝ አትበለኝና አንድ ነገር ልለምንህ ነው? ይህን የመብል የመጠጡን ነገር ተወው፡ ነጭ
ሺልንግም እጨምርልሃለሁ ይቺን መኪና ትጠብቅልኛለህ አልኩት።
«ፍየሎቼን ማን ያግድልኛል?» ብሎ መለሰልኝ፡፡ ጓደኛም የለህ እንዴ?
ካለህ ፍየሎቻችሁን ተራ በተራ እየመለሳቹ መኪና ትጠብቁልኛላችሁ» ከማለቴ ጓደኛስ አለኝ» አለኝ፡፡ “ሒድ በል ጥራውና ና » ብዬ በትሕትና አዘዝኩት፡፡ በቀጭኗ መንገድ ወደ ጫካው ወስተ ሄደ፡፡ ወደ ጉድጓድ እንደሚገባ ሰው ጭንቅላቱ ቁልቁል ስለ ወረደች አካባቢው ተዳፋት
እንደሆነ ገባኝ፡፡ ከየወዲያነሽ ጋር የሚረባ ወሬ እንኳ ሳናወራ ጥጆችና ጊደሮች
እየነዱ ከተፍ አሉ፡፡ በመጀመሪያዉ ልጅና በሁለተኛው ልጅ መካከል ትንሽ
የመልክ ልዩነት እንጂ በአለባበስና በአረማመድ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ሁለተኛ
ልጅ ፊቱ ሰልከክ ብላ መጠጥ ያለች ነች፡፡ አፍንጫው ሰልካካ ፀጉሩ ጥቁር
ለስላሳ ነው፡፡ ቆሸሽ ባለችው የእጀ ጠባቡ ኪሶች ኣካባባና እጅጌዎቹ ላይ ልዩ
ልዩ አዝራሮች ተተክለዋል። ሁለቱም ግራና ቀኝ ቆመው እንጠብቅላችኋልን አሉ፡፡
«እንግዲህ አደራችሁን ስመለስ የማደርግላችሁን አታውቁትም አልኩና መኪናይቱን ከፍቼ ምግብና መጠጥ የያዘውን መጠነኛ የእቃ ሻንጣ
አወጣሁ፡፡
ደስ እንዲላቸውኛ በሚያጓጓ ተስፋ እንዲጠብቁልኝ በማሰብ ሁለት
ሁለት ዳቦና አንዳንድ ብርቱካን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ያች በየጊዜው የምትጠገነውና የማያዘልቅ የገንዘብ መፍጃ ዕድሳት
የሚደረግላት የጉልላት ቮልስዋገን እየተንገጫገጨች መንቆርሰሷ አልቀረም፡፡
አውላላ ሜዳ ላይ ታጋልጠኛለች በማለት ሆዱን ቅር ያለው ዕለት በታክሲና በእግሩ መሔድ ይቀናዋል። አንዳንድ ቀን ተገፍታም ይሁን በበርቺ በርቺ
ተንቀሳቅሳ መሽከርከሯ ስለማይቀር እየተንገራገጨችም ቢሆን ይነዳታል፡፡
መንገድ ላይ ቀጥ ባለች ቁጥር ደግሞ ከየትም ለቃቅሞ ያገዛቸውን ልዩ ልዩ
መፍቻዎች፣ የብረታ ብረት ቅባት ካጠገበ አሮጊ ከረጢት ውስጥ ይዘከዝክና
ለማጠባበቅ ወደ ሞተሯ ይገሠግሣል። ምን ያደርጋል ታዲያ! ያን ውስብስብና
ቁልፍልፍ የብረት ቁልል ሲያይ “አሁን ደግሞ የትኛው ይሆን? ምን ዐይነት
ፍርጃ ነው! » ይልና አንዱን መፍቻ ወርውሮ እንቺ ቅመሽ ይላታል። በዚያው
ደግሞ ሌላ ዕቃ ይቀለጠምና ከናካቴው እንደ አበያ በሬ ለጥ ትላለች፡፡
ከተማዉ ውስጥ ያሉት ሽቃዮች የተሰናከለች ተሽከርካሪ አነፍንፈው ማግኘት ይችሉ ይመስል ወዲያውኑ እንደ ጉንዳን ይከቧታል። እሺ ካለች አለች፡
አለበለዚያም በምንጭሯ አስጎትቶም ይሁን ከወደ ጅራቷ አስጠምዞ አንዱ ጋ
አስጠግቷት ይሔዳል። ለገፉለትም ሆነ ለሳቡለት ሰዎች ስለት እንዳለበት ሰው
የሚሰጠውን ሰጥቶና ኣንጀቱን አሳርሮ በእግሩ ሲንገላወድ የነቀሉት ጭሰኛ
ይመስላል፡፡
እንድ ሰሞን ጥርሱን ነክሶ ስላሳደሳት የመኪና ወጉ ደርሷት ደኅና ስትሽከረከር ሰነበተች። እሱም ሠጋር በቅሉ ላይ እንደ ተቀመጠ የዱሮ መኳንንት ውስጧ ገብቶ ጉብ ይላል፡፡ የወዲያነሽ ጋር ሽርሽር ለመሔድ አስበን ስለ ነበር መኪናውን እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፡፡ 'ውሰድ አለ ቃሉን
ሠፈር አድርጎ በደኅንነቷ እየተመካ፡፡ «በዚህ ሰሞን ውቃቢ ቀርቧታል፡፡
እንዳጋጣሚ ግን በመሏ መጥቶ እንዱ ጋ ቀጥ ብላ ጉድ ካደረገችህ የራስህ
ጉዳይ ነው የለሁበትም!» ብሉኝ ቅዳሜ ማታ ወሰድኳት።
እኔና የወዲያነሽ ከንጋቱ አስራ አንድ ሰዓት እንደሆነ ለሁለታችን የሚበቃ ጥቂት ለስላሳ መጠጥና ምግብ ጭነን ከአዲስ አበባ ውጪ ወደ ጎጃም መንገድ ሰማንያ አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ተጓዝንባት፡፡ ምንም እንከንና ጉድለት ሳያጋጥመን ካሰብነው ቦታ እስክንደርስ ድረስ መኪናይቱን እያቆምኩ ባሻገር የሚታዩትን ተራሮችና ኮረብቶች ለጥ ያሉ ለምለም ሜዳዎችና የሽልጥልጥ ሸንተራራማ ገደሉች እያየን፡፡ ምቹ ቦታና መዝናኛ ነው ብዬ ከገመትኩት ሥፍራ ላይ እንደ ደረስኩ የመንገዱን ዳር አስይዤ አቆምኳት፡፡ያ ብዙ ቦታ ላይ በንዝረት የሚገጫገጨው ልል የብረታ ብረት ክፍል ጊዜያዊ ጸጥታ አገኘ። የመኪናይቱ ሙቀት ቀስ በቀስ ቀነሰ። የውስጧ ሞቃት አየር
በመስኮት በኩል በሚገባው ቀዝቃዛ አየር የተገፋ ቦታ ይለቃል፡፡ የመኪናይቱ
ፊት ወደ ሰሜን በመዞሩ በስተምሥራቅ በኩል ባለው መስኮት በከፍተኛ
ፍጥነት እየተግለበለበ የሚገባው አየር በትይዩው መስኮት እየተዥጎደጎደ
ይፈተለካል። የመኪናይቱ መሪ በስተግራ በኩል በመሆኑ የወዲያነሽን እየዳበሰ
የሚመጣው አየር ከላይዋ ላይ የለሰለሰ የሽቶ መዓዛ ያመጣና አወድወድ አድርጎኝ ይከተለባል። ባለፈው አየር እግር የሚተካው አየር ይክሰኛል። በእኔ በኩል ያለውን በር ከፍቼ እግሬን ወደ ውጪ ዘርግቼ ራሴን በየወዲያነሽ ጭን
ላይ አሳረፍኩት፡፡ አንጋጥጬ ስመለከታት አዘቅዝቃ አየችኝ፡፡ አዝራሮቼ በተከፈቱበት በኩል ቀኝ እጅዋን አሾልካ ደረቴን ስትደባብሰኝ የፍቅራዊ ደስታ ሰመመን አጥለቀለቀኝ፡፡ ጋደም እንዳልኩ ዐይኖቼ ተንገረገቡ፡፡ ዐሥራ አምስት ደቂቃ ያህል ቀ-ም እንዳደረግሁ ወደ ከተማ በሚያዘግም የጭነት መኪና ድምፅ ባንኜ ነቃሁ፡፡ ጥቂት ምዕራፎች ወደፊት ነዳሁ።
እንደገና ከመንገድ ገለል አድርጌ አቆምኳት። ሠላሳ ርምጃዎች ያህል
ወጣ ብዬ ስለ ነበር አንዳንድ አጫጭር ቁጥቋጦዎች በመኪናይቱ ተቀለጣጠሙ ጎማው የተሽከረከረባቸው በዚያው ሲቀሩ በመኪናይቱ ሆድ የተለመሰሉት ግን በመጠኑ ጎበጥበጥ ብለው ቀኑ፡፡ ከፊት ለፊታችን ጥቅጥቅ ያለ አጋምና ብሳና ድግጣና ምሥርች ዐልፎ ዐልፎ ኮርች በቅሉ አካባቢውን አይደፈር መሳይ ግርማ አልብሶታል። ወደ ዱሩ የምታስኬደው ቀጭን መንገድ ባረንጓዴ ወረቀት ላይ የተሰመረች ግራጫ መስመር ትመስላለች፡፡በዚቹ መንገድ በኩል ይዣት ልግባ ይሆን ይቅርብኝ እያልኩ ሳመነታ'
ስፈራና ስጠራጠር ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡
አንድ ውሳኔ ለመወሰን ጫካውን አፍጥጬ ስመለከት ጥቂት ራቅ
ብሎ አንድ አፈርቻና ሦስት አራት ያህል ዝንጉርጉር እንስሳት ከጫካው ውስጥ ተከታትለው ብቅ አሉ፡፡
ለጊዜው ልብ ብዬ ባለማየቴ ደንገጥ አልኩና «ምንድናቸው?» አልኩ።
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል ያደረገችው የወዲያነሽ «ፍየሉች ናቸው» አለችኝ፡፡
«እኔስ ሌላ ነገር መስለውኝ» ብዩ ነገሩን ወዲያ ወዲህ እምታታሁ፡፡ ደግነቱ
ስሜቴን ስላላወቀችብኝ ዝም አለች። ጥሎ አይጥሌ ሲረዳኝ አንድ እረኛ ብዙ
ፍየሎች እያንጋጋ ከጫካው ውስጥ ብቅ አለ፡፡ ከመኪና ወጥተን የየወዲያነሽን
እጅ ያዝ አድርጌ እንደቆምኩ እረኛው አጠገባችን ደረሰ። ደረቱ ላይ ሰፋ-ሰፋ
ያለ ኪሶች ያለባት የአቡጀዲ እጀ ጠባብ ለብሷል። የሁለቱም ኪሶቹ አፍ አደፍደፍ ብሎ ጠቁሯል። ሁለት ፍየሎች ተነጥለው ወደ ሌላ አቅጣጫ ስለሄዱ እነሱን ለመመለስ ነይ እሪያ!» ብሎ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ልብሱ ከበስተኋላው ቂጡ ላይ ድልህ የነካው ጋቢ መስሏል።
ከጉልበቱ በታች ያለው ሙጭርጭር በደረቀ ጭራሮ የተጠረገ የረገጥ ቤት መስሏል፡፡ በግራ ብብቱ ቀጠን ያለች ብትር አጣብቆ ይዟል። ዋሽንቱን በእጁ ውስጥ እያንከባለለ ያሻሻታል። ፍየሎቹ እየቀነጣጠቡ በአጠገባችን አለፉ፡፡ እረኛውም ከኋላ ከኋላቸው ከተፍ አለ። ልብሱ ላይ ዐልፎ ዐልፎ ጨጎጊት ተጣብቋል። አጋም ሲቃቅምበት የዋለው ከንፈሩ ጠቋቀሯል። እንኩታ ሲቸችግ የዋለ መስሏል።
ለስለስ ባለ ድምፅ "አንተ ልጅ ና እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ አልኩት፡፡ ነባር ፍርሃት ሳይሆን የጥርጣሬ ፍርሃት በፊቱ ላይ እየታየ በዝግታ መጥቶ ቆመ ወደ ጫካው እያመላከትኩት በዚ ጫካ ውስጥ መንገድ አለ እንዴ?ብዬ ጠየኩት? 'አዎ' ብሎ ባጭሩ መለሰልኝ፡፡
«እንግዲያውማ እዚ ቅርቡ መናፈስ ይቻላል፣ አስቸገሩኝ አትበለኝና አንድ ነገር ልለምንህ ነው? ይህን የመብል የመጠጡን ነገር ተወው፡ ነጭ
ሺልንግም እጨምርልሃለሁ ይቺን መኪና ትጠብቅልኛለህ አልኩት።
«ፍየሎቼን ማን ያግድልኛል?» ብሎ መለሰልኝ፡፡ ጓደኛም የለህ እንዴ?
ካለህ ፍየሎቻችሁን ተራ በተራ እየመለሳቹ መኪና ትጠብቁልኛላችሁ» ከማለቴ ጓደኛስ አለኝ» አለኝ፡፡ “ሒድ በል ጥራውና ና » ብዬ በትሕትና አዘዝኩት፡፡ በቀጭኗ መንገድ ወደ ጫካው ወስተ ሄደ፡፡ ወደ ጉድጓድ እንደሚገባ ሰው ጭንቅላቱ ቁልቁል ስለ ወረደች አካባቢው ተዳፋት
እንደሆነ ገባኝ፡፡ ከየወዲያነሽ ጋር የሚረባ ወሬ እንኳ ሳናወራ ጥጆችና ጊደሮች
እየነዱ ከተፍ አሉ፡፡ በመጀመሪያዉ ልጅና በሁለተኛው ልጅ መካከል ትንሽ
የመልክ ልዩነት እንጂ በአለባበስና በአረማመድ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ሁለተኛ
ልጅ ፊቱ ሰልከክ ብላ መጠጥ ያለች ነች፡፡ አፍንጫው ሰልካካ ፀጉሩ ጥቁር
ለስላሳ ነው፡፡ ቆሸሽ ባለችው የእጀ ጠባቡ ኪሶች ኣካባባና እጅጌዎቹ ላይ ልዩ
ልዩ አዝራሮች ተተክለዋል። ሁለቱም ግራና ቀኝ ቆመው እንጠብቅላችኋልን አሉ፡፡
«እንግዲህ አደራችሁን ስመለስ የማደርግላችሁን አታውቁትም አልኩና መኪናይቱን ከፍቼ ምግብና መጠጥ የያዘውን መጠነኛ የእቃ ሻንጣ
አወጣሁ፡፡
ደስ እንዲላቸውኛ በሚያጓጓ ተስፋ እንዲጠብቁልኝ በማሰብ ሁለት
ሁለት ዳቦና አንዳንድ ብርቱካን
👍2
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...እንደ ረጂም ነጭ ጭራ የዕንጨት ሽበት ያንጠለጠሉ ዛፎች በብዛት ይታያሉ፡፡ የማዶውን ትቼ አጠገቤ ስመለከት ትልልቅ ጐለጐሎች የሞተች
የእባብ ራስ (ትል) ጉማጅ አግኝተው ከፊትና ከኋላ በመተጋገዝ እያንከባለሉና
እየገፉ ሲወስዷት አየሁ። ሕይወት እና ኑሮ የከባድ ትግል ውጤት ናቸው::የቦታው ቁልቁለታማ ስበት ከጉልበታቸው በላይ በማየሉ አምልጣቸው ተንከባለለች፡፡ የት እንዳረፈችና እንደገባች ስላጧት ተቅነዘነዙ። እንደ ፈሪ መርዶ ነጋሪ ዙሪያውን ዞሩ። በፍለጋ ብዛት አገኟት፡፡
ተፈጥሮ ለታካች ከማዕዷ አታጎርስምና እንደገና በትግል ይዘዋት መንገድ ቀጠሉ ፍጻሜያቸውን ለማወቅ በዐይኖቼ ተከተልኳቸው:: በአንዲት ሰፊ ደረቅ ቅጠል ሥር ከነግዳያቸው ተሸጎጡ፡፡ የእንሱ ጉዳይ በዚያው አከተመ።
የየወዲያነሽ አእምሮ ምን እንደሚያስብና እንደሚያሰላስል ባላውቅም አካባቢውን በፈገግታ ትመለከተዋለች። ድንገት ሳታስበው ክንዷን ሳብ አድርጌ
«የወዲያ! ይኸ አካባቢ ደስ አይልም እንዴ? አልኳት፡፡ በአድናቂ ስሜት ፈገገ
አለች።
ሻንጣውን ከጐኗ ሳብ አድርጋ ትውስብሳቢውን ተረተረችው:: አምስት
ብርቱካኖች አውጥታ እንደ ምፅዋት መቀበያ ሰጣ በተን ባለው ነጠላዋ ላይ
አስቀመጠች:: እናት ነች የልብ ከውቃ:: መላጥ ጀመርኩ፡፡ እሷም ተያያዘችው:: እርሷ ገና ልጣ ሳታጋምስ እኔ ለእሷ ሦስት ጊዜ ለራሴ ሁለቴ ጎረስኩ፡፡ አንዷን የብርቱካን ፍንካች አፌ ውስጥ እያንከላወስኩ «የወዲያ ደስ አላለሽም መሰል ይህ አካባቢ?» ብዬ እንደገና ጠየቅኋት። በጠይሙ ፊቷ ላይ
ፈገግታዋ እየተዘናከተ «እንዴት ብዬ ልንገርህ?» ብላ በእጅዋ የያዘቻትን
ፍንካች ሰለከከች። እኔ ሁለተኛዬን በልቼ ልጨርስ ስል እርሷ ሁለተኛይቱን
ልጣ ፈረካከሰቻት። «እንካ እስኪ ይቺን ቅመሳት ጌትዬ?» አለችኝ።
“አ!” ብዬ ተቀበልኳት። ከእጅዋ ላይ ተጨማሪ ጣዕም ፈልቆ ብርቱካኑ ውስጥ የገባ ይመስል ያጎረሰችኝ ጣፈጠኝ። ስውጥ አይታ ደገመችኝ። ቁልቁል ሸኘኋት፡፡ በድጋሚ ስትዘረጋ «ተይ ተይ በቃኝ! አንቺ ጉረሻት» አልኳት። እጅዋን እንደ ዘረጋች «ይቺን ብቻ ጌትዬ ስሞትልህ?» ስትለኝ ካንገት በላይ እየተግደረደርኩ ተቀበልኳት። ሆዴ ብቻ ሳይሆን ሕሊናዬም ጠገበች፡፡ ደመናኑን በረጅም መጥረጊያ ሙልጭ አድርገው የጠረጉት ይመስል ሰማዩ ጸጥ ያለ ባሕር መስሏል። ምንም እንኳ በሰማዩ ላይ ደመና ባይታይ ፀሐይዋን ለማየት የቻልነው ገላጣው ቦታ ላይ በመቀመጣችን ነበር፡፡
እኩለ ቀን ሊሞላ አንድ ሰዓት ብቻ ቀርቶታል። ኃይለኛውን የበጋ ሐሩር የቀነሰልን ግን ከአካባቢው የሚነፍሰው የለስላሳ አየር ሽውታ ነበር፡፡
ከነበርንበት ሥፍራ ተነሥተን ጥቂት ርምጃዎች ወደ ጎን አለፍ ብለን ከአንድ
ቁጥቋጦ ሥር ተቀመጥን፡፡ የቁጥቋጦው ቅጠል የላይ ገጽ በጣም ደማቅ አረንጓዴ ሆኖ ወበቅ እንዳቃጠለው የከበርቴ ፊት
በስተጀርባው ግን ግርጣት ያይልባታል።
ወዛም እንደ ቀድሞ ገዳይ ጎፈሬ የተቸመቸመው ድፍን አረንጓዴ ቅጠሏና
ደርበብ ያለው ቁመቷ ታይቶ የማይጠገብ የውበት ፀጋ አልብሷታል፡፡
የወዲያነሽ አንዷን ጎበጥ ብላ መሬት ለመንካት አንድ ክንድ ያህል የማይቀራትን ቅርንጫፍ እንደ ተቀመጠች ተንጠራርታ ሳበቻትና ለጋ ጫፉን ቀለጠመቻት፡፡ በቀኝ እጅዋ ይዛ ግራ እጅዋ ላይ ስትጠበጥባት ጥቂት ቅጠሎች ረገፉ፡፡
አንዷን በጥቃ ተስተካክለው በሰቀሉት ጥርሶቿ እየነካከሰች በሳቻት።
ቅጠሊቱን ከእጅዋ ላይ መንጭቄ ወረወርኩና «ምን ዐይነቷ ናት እባካችሁ?
እስኪ አሁን ምኑን አውቀሽው ነው? ምናልባትስ መርዘኛ ቅጠል ቢሆን?»
አልኩና ከአንጀት ያልመጣ ቁጣ ተቆጣሁ፡፡ ሣቅ ብላ ትንሿን ጣቴን ያዘችና
«መጥፎ ቅጠል መሰለህ እንዴ? እኔ እኮ ዱሮውንም ቢሆን አውቀዋለሁ፡፡
አንተ አታውቀውም መስል? ደደሆ እኮ ነው:: ምን ያደርጋታል ብለህ ነው?
አለችኝ።
አለማወቄን ለመሰወር ያህል ነው እንዴ? እኔ እኮ ከረሳሁት ቆይቻለሁ» አልኳት ቀድሞዉንም ቢሆን የማላውቀውን ቅጠል፡፡ እንደማላውቀው አውቃብኛለች፡፡ አሁንም ያንኑ ቅጠል በጥሳ በጥርሷ
ወጋጋችው። እኔም ለመቅመስ ያህል አራት አምስቱን ቅጠል አጎርኩት።
ምራቄ ከአፌ ውስጥ በመዘውር ተቀድቶ የተወሰደ ይመስል አፌ ኩበት ሆነ፡፡
ምላሴ ደረቀች። ላንቃዬ እንደ ተወቀረ ወፍጮ ሞዠቀኝ። ውስጥ ውስጡን
ጉዴ ፈላ፡፡ እንዳይታወቅብኝ ወሬም የለ ምንም የለ፣ ዝም አልኩ፡፡ዳግመኛ ሌላ ቅርንጫፍ ጎትቼ እመጣለሁ ብላ ስትንጠራራ ጠርዙ ጉልበቷ ላይ ያደረው ቀሚሷ እስከ ጭኗ ተስቦ አሻቀበ፡፡ የወንድነት ንቁ ፍላጎቴ በጠይሙ ውብ ገላዋ ዙሪያ ተንከራተተ፡፡ እጄን ዘርግቼ ለስላሳ ገላዋን ዳበስኩት፡፡ መላ ሰውነቴ ብው ብሎ ጋለ፡፡ ከተቀመጥኩበት ተነሣሁ የወዲያነሽንም አፈፍ ኣድርጌ አስነሣኋት። እኔ ወደ ምዕራብ እርሷ ወደ
ምሥራቅ እያየን ፊት ለፊት ቆምን፡፡ ትከሻዋን ይዤ ደረቴን ወደ ደረቷ
አስጠጋሁት። አቀፈችኝ፡፡ አቀፍኳት። ከልብ ተሳሳምን።
ነፋስ እንደ መነጫጨረው የድርቆሽ ክምር ጸጉሯን በታተንኩት፡፡ ያ ከጥቂት ወራት በፊት አንገቷ ላይ ደርሶ የነበረው ጸጉሯ አድጎ ትከሻዋን ያስሳል፡፡ ጫፍ ጫፉ ተቆልምሞ በመጥመዝመዝ እጆቹን ሽቅብ እንደ ዘረጋ ባሕታዊ ወደ ላይ አንጋጧል። ከከንፈሯ ወረድ ብዩ ያን ካፊያ እንደ መታው ጓሚያ እንኮይ የተውለከለከውን አንገቷን ባፍና በአገጬ አድፈጠፈጥኩት።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ከቁጥቋጦይቱ ውስጥ ወጣን፡፡ አካባቢውን ለማየት ስለ ፈለግን አንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ወጥተን መንገድ ፈለግን፡፡ የወዲያነሽ የለበሰችው ገብስማ ቀሚስና የደረበችው ቢጫ ሹራብ፣ የአካባቢው ዕፅዋት ልምላሜ፣ ምግብ የያዝንበት ቀይ ሻንጣ፣ የታጠቅሁት ሰማያዊ ሱሪና የለበስኩት ሽንብራማ ኮት፣ ባንድነት ሆነው የውበት ሽማ በመዘርጋት በቅልቅል ኀብረ ቀለማቸው አእምሮዬን ስላረኩት ታላቅ ሰብኣዊ ኩራት ተሰማኝ፡፡ ሹራቧንና ነጠላዋን አጣጥፌ ሻንጣ ውስጥ ከጨመርኩ በኋላ ቁልቁለቱን ተያያዝነው:: በጫካው ውስጥ ለውስጥ የሚያስኬደው መንገድ ቡችሎች እንደ ጎተቱት አንጀት የተጥመዘመዘ በመሆኑ በረጂሙ አግድም እንሔድና እንደ ገና ደግሞ ተመልሰን ከነበርንበት ቦታ ግርጌ እንደርሳለን፡፡ልዩነቱ ትንሽ ዝቅ ማለታችን ብቻ ነበር። አንዲት አፈመለከት ቅርፅ ያላት ትንሽ ቢጫ የሐረግ አበባ አገኘሁና ቀጥፌ ዘረጋሁላት፡፡ እጅዋ በድካም እንደ
መዝለፍለፍ እየቃጣው ተቀበለችኝ። መለስ ብዪ «የወዲያ! ያቺ ፀሐይና ይኸ
ቁልቁለት አዛሉሽ መሰል?» አልኳት። «ብዙ ሄጄ ስለማላውቅ ነው መሰል»
ብላ ደማ ፈገግታ አሳየች፡፡
ጥቂት ዝቅ እንዳልን ጆሮዎቼ የመልካም ተስፋ ድምፅ ሰሙ:: ለእኔም ለእርሷም አንጀት የሚያርስ እፎይታ ነበር። ከፊት ለፊታችን ከወደ ጋራው ጥግ ካሉት ትላልቅ የድንጋይ ቋጥኞች ሥር በከፍተኛ ፍጥነት እየተውዘገዘገች የምትወርድ ፏፏቴ ኣየን፡፡
በፏፏቴው ዳርና ዳር ያለው አለት በጥቁርና ጓያ መስል መልኩ
በጣም ይማርካል። ከወንዚቱ ዳርቻ የበቀሉት ዛፎች ቅርንጫፎቻቸው እንደ
ደጋን ጎብጦ ቅጠሎቻቸው ወራጅዋ ውሃ ውስጥ ተዘፍቆ በውሃይቱ ግፊት
ከወዲያ ወዲሀ ይነቃነቃሉ፡፡ ከሸለቆው ውስጥ የትኛው ቦታ ላይ እንደምትመነጭ አይታይም። ኩልል ብሎ የጠራው ውሃ የድንጋዩን መልክ ተጋርቶታል። ወራጂቱ ውሃ ድምፅ ሳታሰማ ጥቂት አግድመት ታገድምና ጥግ ይዞ ጠርብ የመሰለ ድንጋይ ሲያጋጥማት ፏፏቴ ቢጤ ፈጥራ ትፈጠረቃለች።
በፏፏቴው ማረፊያ ዙሪያ የእንዶድ አሪፋ የመሰሉ ነጭ የውሃ ንፍሥሪ ኳሶች ይንሳፈፋሉ፡፡ የጥበትና የስፋታቸው መጠን የተለያየ ቢሆንም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...እንደ ረጂም ነጭ ጭራ የዕንጨት ሽበት ያንጠለጠሉ ዛፎች በብዛት ይታያሉ፡፡ የማዶውን ትቼ አጠገቤ ስመለከት ትልልቅ ጐለጐሎች የሞተች
የእባብ ራስ (ትል) ጉማጅ አግኝተው ከፊትና ከኋላ በመተጋገዝ እያንከባለሉና
እየገፉ ሲወስዷት አየሁ። ሕይወት እና ኑሮ የከባድ ትግል ውጤት ናቸው::የቦታው ቁልቁለታማ ስበት ከጉልበታቸው በላይ በማየሉ አምልጣቸው ተንከባለለች፡፡ የት እንዳረፈችና እንደገባች ስላጧት ተቅነዘነዙ። እንደ ፈሪ መርዶ ነጋሪ ዙሪያውን ዞሩ። በፍለጋ ብዛት አገኟት፡፡
ተፈጥሮ ለታካች ከማዕዷ አታጎርስምና እንደገና በትግል ይዘዋት መንገድ ቀጠሉ ፍጻሜያቸውን ለማወቅ በዐይኖቼ ተከተልኳቸው:: በአንዲት ሰፊ ደረቅ ቅጠል ሥር ከነግዳያቸው ተሸጎጡ፡፡ የእንሱ ጉዳይ በዚያው አከተመ።
የየወዲያነሽ አእምሮ ምን እንደሚያስብና እንደሚያሰላስል ባላውቅም አካባቢውን በፈገግታ ትመለከተዋለች። ድንገት ሳታስበው ክንዷን ሳብ አድርጌ
«የወዲያ! ይኸ አካባቢ ደስ አይልም እንዴ? አልኳት፡፡ በአድናቂ ስሜት ፈገገ
አለች።
ሻንጣውን ከጐኗ ሳብ አድርጋ ትውስብሳቢውን ተረተረችው:: አምስት
ብርቱካኖች አውጥታ እንደ ምፅዋት መቀበያ ሰጣ በተን ባለው ነጠላዋ ላይ
አስቀመጠች:: እናት ነች የልብ ከውቃ:: መላጥ ጀመርኩ፡፡ እሷም ተያያዘችው:: እርሷ ገና ልጣ ሳታጋምስ እኔ ለእሷ ሦስት ጊዜ ለራሴ ሁለቴ ጎረስኩ፡፡ አንዷን የብርቱካን ፍንካች አፌ ውስጥ እያንከላወስኩ «የወዲያ ደስ አላለሽም መሰል ይህ አካባቢ?» ብዬ እንደገና ጠየቅኋት። በጠይሙ ፊቷ ላይ
ፈገግታዋ እየተዘናከተ «እንዴት ብዬ ልንገርህ?» ብላ በእጅዋ የያዘቻትን
ፍንካች ሰለከከች። እኔ ሁለተኛዬን በልቼ ልጨርስ ስል እርሷ ሁለተኛይቱን
ልጣ ፈረካከሰቻት። «እንካ እስኪ ይቺን ቅመሳት ጌትዬ?» አለችኝ።
“አ!” ብዬ ተቀበልኳት። ከእጅዋ ላይ ተጨማሪ ጣዕም ፈልቆ ብርቱካኑ ውስጥ የገባ ይመስል ያጎረሰችኝ ጣፈጠኝ። ስውጥ አይታ ደገመችኝ። ቁልቁል ሸኘኋት፡፡ በድጋሚ ስትዘረጋ «ተይ ተይ በቃኝ! አንቺ ጉረሻት» አልኳት። እጅዋን እንደ ዘረጋች «ይቺን ብቻ ጌትዬ ስሞትልህ?» ስትለኝ ካንገት በላይ እየተግደረደርኩ ተቀበልኳት። ሆዴ ብቻ ሳይሆን ሕሊናዬም ጠገበች፡፡ ደመናኑን በረጅም መጥረጊያ ሙልጭ አድርገው የጠረጉት ይመስል ሰማዩ ጸጥ ያለ ባሕር መስሏል። ምንም እንኳ በሰማዩ ላይ ደመና ባይታይ ፀሐይዋን ለማየት የቻልነው ገላጣው ቦታ ላይ በመቀመጣችን ነበር፡፡
እኩለ ቀን ሊሞላ አንድ ሰዓት ብቻ ቀርቶታል። ኃይለኛውን የበጋ ሐሩር የቀነሰልን ግን ከአካባቢው የሚነፍሰው የለስላሳ አየር ሽውታ ነበር፡፡
ከነበርንበት ሥፍራ ተነሥተን ጥቂት ርምጃዎች ወደ ጎን አለፍ ብለን ከአንድ
ቁጥቋጦ ሥር ተቀመጥን፡፡ የቁጥቋጦው ቅጠል የላይ ገጽ በጣም ደማቅ አረንጓዴ ሆኖ ወበቅ እንዳቃጠለው የከበርቴ ፊት
በስተጀርባው ግን ግርጣት ያይልባታል።
ወዛም እንደ ቀድሞ ገዳይ ጎፈሬ የተቸመቸመው ድፍን አረንጓዴ ቅጠሏና
ደርበብ ያለው ቁመቷ ታይቶ የማይጠገብ የውበት ፀጋ አልብሷታል፡፡
የወዲያነሽ አንዷን ጎበጥ ብላ መሬት ለመንካት አንድ ክንድ ያህል የማይቀራትን ቅርንጫፍ እንደ ተቀመጠች ተንጠራርታ ሳበቻትና ለጋ ጫፉን ቀለጠመቻት፡፡ በቀኝ እጅዋ ይዛ ግራ እጅዋ ላይ ስትጠበጥባት ጥቂት ቅጠሎች ረገፉ፡፡
አንዷን በጥቃ ተስተካክለው በሰቀሉት ጥርሶቿ እየነካከሰች በሳቻት።
ቅጠሊቱን ከእጅዋ ላይ መንጭቄ ወረወርኩና «ምን ዐይነቷ ናት እባካችሁ?
እስኪ አሁን ምኑን አውቀሽው ነው? ምናልባትስ መርዘኛ ቅጠል ቢሆን?»
አልኩና ከአንጀት ያልመጣ ቁጣ ተቆጣሁ፡፡ ሣቅ ብላ ትንሿን ጣቴን ያዘችና
«መጥፎ ቅጠል መሰለህ እንዴ? እኔ እኮ ዱሮውንም ቢሆን አውቀዋለሁ፡፡
አንተ አታውቀውም መስል? ደደሆ እኮ ነው:: ምን ያደርጋታል ብለህ ነው?
አለችኝ።
አለማወቄን ለመሰወር ያህል ነው እንዴ? እኔ እኮ ከረሳሁት ቆይቻለሁ» አልኳት ቀድሞዉንም ቢሆን የማላውቀውን ቅጠል፡፡ እንደማላውቀው አውቃብኛለች፡፡ አሁንም ያንኑ ቅጠል በጥሳ በጥርሷ
ወጋጋችው። እኔም ለመቅመስ ያህል አራት አምስቱን ቅጠል አጎርኩት።
ምራቄ ከአፌ ውስጥ በመዘውር ተቀድቶ የተወሰደ ይመስል አፌ ኩበት ሆነ፡፡
ምላሴ ደረቀች። ላንቃዬ እንደ ተወቀረ ወፍጮ ሞዠቀኝ። ውስጥ ውስጡን
ጉዴ ፈላ፡፡ እንዳይታወቅብኝ ወሬም የለ ምንም የለ፣ ዝም አልኩ፡፡ዳግመኛ ሌላ ቅርንጫፍ ጎትቼ እመጣለሁ ብላ ስትንጠራራ ጠርዙ ጉልበቷ ላይ ያደረው ቀሚሷ እስከ ጭኗ ተስቦ አሻቀበ፡፡ የወንድነት ንቁ ፍላጎቴ በጠይሙ ውብ ገላዋ ዙሪያ ተንከራተተ፡፡ እጄን ዘርግቼ ለስላሳ ገላዋን ዳበስኩት፡፡ መላ ሰውነቴ ብው ብሎ ጋለ፡፡ ከተቀመጥኩበት ተነሣሁ የወዲያነሽንም አፈፍ ኣድርጌ አስነሣኋት። እኔ ወደ ምዕራብ እርሷ ወደ
ምሥራቅ እያየን ፊት ለፊት ቆምን፡፡ ትከሻዋን ይዤ ደረቴን ወደ ደረቷ
አስጠጋሁት። አቀፈችኝ፡፡ አቀፍኳት። ከልብ ተሳሳምን።
ነፋስ እንደ መነጫጨረው የድርቆሽ ክምር ጸጉሯን በታተንኩት፡፡ ያ ከጥቂት ወራት በፊት አንገቷ ላይ ደርሶ የነበረው ጸጉሯ አድጎ ትከሻዋን ያስሳል፡፡ ጫፍ ጫፉ ተቆልምሞ በመጥመዝመዝ እጆቹን ሽቅብ እንደ ዘረጋ ባሕታዊ ወደ ላይ አንጋጧል። ከከንፈሯ ወረድ ብዩ ያን ካፊያ እንደ መታው ጓሚያ እንኮይ የተውለከለከውን አንገቷን ባፍና በአገጬ አድፈጠፈጥኩት።
እጅ ለእጅ ተያይዘን ከቁጥቋጦይቱ ውስጥ ወጣን፡፡ አካባቢውን ለማየት ስለ ፈለግን አንድ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ወጥተን መንገድ ፈለግን፡፡ የወዲያነሽ የለበሰችው ገብስማ ቀሚስና የደረበችው ቢጫ ሹራብ፣ የአካባቢው ዕፅዋት ልምላሜ፣ ምግብ የያዝንበት ቀይ ሻንጣ፣ የታጠቅሁት ሰማያዊ ሱሪና የለበስኩት ሽንብራማ ኮት፣ ባንድነት ሆነው የውበት ሽማ በመዘርጋት በቅልቅል ኀብረ ቀለማቸው አእምሮዬን ስላረኩት ታላቅ ሰብኣዊ ኩራት ተሰማኝ፡፡ ሹራቧንና ነጠላዋን አጣጥፌ ሻንጣ ውስጥ ከጨመርኩ በኋላ ቁልቁለቱን ተያያዝነው:: በጫካው ውስጥ ለውስጥ የሚያስኬደው መንገድ ቡችሎች እንደ ጎተቱት አንጀት የተጥመዘመዘ በመሆኑ በረጂሙ አግድም እንሔድና እንደ ገና ደግሞ ተመልሰን ከነበርንበት ቦታ ግርጌ እንደርሳለን፡፡ልዩነቱ ትንሽ ዝቅ ማለታችን ብቻ ነበር። አንዲት አፈመለከት ቅርፅ ያላት ትንሽ ቢጫ የሐረግ አበባ አገኘሁና ቀጥፌ ዘረጋሁላት፡፡ እጅዋ በድካም እንደ
መዝለፍለፍ እየቃጣው ተቀበለችኝ። መለስ ብዪ «የወዲያ! ያቺ ፀሐይና ይኸ
ቁልቁለት አዛሉሽ መሰል?» አልኳት። «ብዙ ሄጄ ስለማላውቅ ነው መሰል»
ብላ ደማ ፈገግታ አሳየች፡፡
ጥቂት ዝቅ እንዳልን ጆሮዎቼ የመልካም ተስፋ ድምፅ ሰሙ:: ለእኔም ለእርሷም አንጀት የሚያርስ እፎይታ ነበር። ከፊት ለፊታችን ከወደ ጋራው ጥግ ካሉት ትላልቅ የድንጋይ ቋጥኞች ሥር በከፍተኛ ፍጥነት እየተውዘገዘገች የምትወርድ ፏፏቴ ኣየን፡፡
በፏፏቴው ዳርና ዳር ያለው አለት በጥቁርና ጓያ መስል መልኩ
በጣም ይማርካል። ከወንዚቱ ዳርቻ የበቀሉት ዛፎች ቅርንጫፎቻቸው እንደ
ደጋን ጎብጦ ቅጠሎቻቸው ወራጅዋ ውሃ ውስጥ ተዘፍቆ በውሃይቱ ግፊት
ከወዲያ ወዲሀ ይነቃነቃሉ፡፡ ከሸለቆው ውስጥ የትኛው ቦታ ላይ እንደምትመነጭ አይታይም። ኩልል ብሎ የጠራው ውሃ የድንጋዩን መልክ ተጋርቶታል። ወራጂቱ ውሃ ድምፅ ሳታሰማ ጥቂት አግድመት ታገድምና ጥግ ይዞ ጠርብ የመሰለ ድንጋይ ሲያጋጥማት ፏፏቴ ቢጤ ፈጥራ ትፈጠረቃለች።
በፏፏቴው ማረፊያ ዙሪያ የእንዶድ አሪፋ የመሰሉ ነጭ የውሃ ንፍሥሪ ኳሶች ይንሳፈፋሉ፡፡ የጥበትና የስፋታቸው መጠን የተለያየ ቢሆንም
👍4❤2😁1
A:
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....እሑድ ከሰዓት በኋላ.….ስለ ለጎ ሐይቅ ከተማና አካባቢዋ ኣንድ ባንድ ካወራችልኝ በኋላ የሕሊናዋን ትዝታ ወደ ደሲ መልሳ ስለ በርበሬ ገንዳ ሙጋድ፣ ዳውዶ ገራዶ፣ ሆጤ፤ ሶሳ፣ አዘዋ ገደል ሰኞ ገበያ…. ነገረችኝ፡፡ «ቆየኝ ደግሞ ሥራዬን ጨርሼ ልምጣና አወራልሃለሁ» ብላ ካልጋው ጫፍ ላይ ሸርተት ብላ ሔደች፡፡ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ሥራዋን አጠናቃ ከተፍ አለች::ነጣ ያለ ቦላሌና ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሼ አልጋው ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ
የጋሻዬነህን ሥዕል አንጋጥጬ ስመለከት ደረሰች፡፡ ሲሠውረኝ አላየችብኝም፡፡
ትከሻዬ ሥር ጣል አድርጌ ተኛሁበት፡፡ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ በሆዴ
ላይ እጂን አሻግራ በመመርኮዝ ከደረቷ ዘንበል አለች፡፡ ትከሻዋ ላይ የነበረችው ባለ አረንጓዴ ጥለት ያንገት ልብስ ተንሸራተተችና የተዘረጋችውን እጅዋን ሸፈነቻት፡፡ ከደረቴ በታች የሆዴ አካባቢ በድንኳን ውስጥ ያላ ነጭ አግዳሚ መቀጫ መሰለ፡፡
ያን በሆዴ ላይ ዐልፎ አልጋው ላይ እንደ ካስማ የተተከለውን እጅዋን በቀኝ እጄ እያሻሽሁ ምናልባት ቅር ይላት ይሆን? በማለት ስፈራ ስቸር ከቆየሁ በኋላ የወዲያ፣ አንድ ነገር ብጠይቅሽ ቅር ይልሻል?» አልኳት፡፡ አሽቆልቁላ ዐይን ዐይኔን ትክ ብላ እያየች ምንስ ነገር ብትጠይቀኝ ምን ብዬ እቀየማለሁ? ስል ጠይቀኝ ልንገርህ? ብላ አቀማመጡዋን አመቻቸች።
ለሁለት ደቂቃ ያህል ውስጥ ውስጡን ሐሳቢን አንቀረቀብኩ፡፡ እንግዲህ
ያለችውን ትበል አልኩና «የወዲያ! ለምን አስታወስከኝ ኣትበይና፣ እናትና
አባትሽ ሲሞቱ የስንት ዓመት ልጅ ነበርሽ?» አልኳት። ፈገግታዋን የቅሬታ
ደም ስለ በረዘው ፊቷ ፈዞ የክረምት ዋዜማ መሰለ፡ ውስጥ ውስጡን ራሴን
«ጌታነህ! የተዳፈነ የኅዘን ረመጥ ጫርክ፣ ያንቀላፋ ኀዘን ቀሰቀስክ» ብዩ ወቀስኩ፡፡ ደቂቃዎች ሠገሩ። ትንሽ ፈነከነክ ብላ «ምነው ምን ነካሀና ኖረሀ ኖረህ ጠየቅኸኝ?» ብላ ፊቷን የትካዜ ዐመድ ነሰነሰችበት፡፡ ካኣሁን አሁን ትጀምራለች በማለት አሰፍስፌ ጠበቅሁ፡፡ ያን እንደ አተር እምቡጥ እበጥ ብሎ የቆየ የታች ከንፈሯን በላይኛው ውብ ጥርሷ ረመጠጠችው። አንድ ጊዜ
አፈትልኮ የተነገረን ሐሳብ መልሶ መዋጥ የማይቻል በመሆኑ ችሎታዩ ከዝምታ ሊያልፍ አልቻለም። እየር ስትስብና ስታስወጣ ከፍና ዝቅ የሚለውን
ደረቷን በመመልከት ላይ እንዳለ «አባቴ ሲሞት አንዲት ፍሬ ልጅ ነበርኩ
አሉ፡፡ ትንሽ ትንሽ እንደ ሕልም ትዝ ይለኛል፡፡ እናቴም አባትሽ ከልጆቹ
ሁሉ አንቺን ይወድሽ ነበር፡፡ ሳይንት እሚባል አገር ካሉት ዘመዶቹ መኻል
የሚወዳትን አክስቱን ስለምትመስዪ የእርሷ ነገር ሆነበትና 'የወዲያነሽ የወዲያ
ሰው ብሎ ስም አወጣልሽና የወዲያዬ የወዲያነሽ አልንሽ ብላ ነገረችኝ። ልጅ
ስለ ነበርኩ ሁሉንም ኣላስታውስም እንጂ አባቴ ብዙ ጊዜ ታሞና ማቆ ማቆ
ነው የሞተው። የሞተ ዕለት ሰዎች ሁሉ ሲያለቅሱ አይቼ እኔም ትንሽ
አልቅሻለሁ፡፡ ሞት ምን እንደሆነ ስለማላውቅ ሄዶ የሚመለስ እንጂ በዚያው የሚቀር አይመስለኝም ነበር፡፡ ሬሳውን በአልጋ ይዘው ከቤት ሲወጡ ምንም ስላልመሰለኝ ጉድሮዬን እያዘናፈልኩ ከመንደሩ ልጆች ጋር እቦርቅ ነበር፡፡
ታናሽ እኅቴ እማዋይሽ ክርስትና የተነሣች ዕለት መጥተው የነበሩት ቄሶች ራሱ የቀብሩም ዕለት መጥተው ስለነበር ለደስታ የመጡ እንጂ ለሌላ ነገር
የመጡ አልመሰለኝም። እያደር ግን ዋል አደር ስል ዕንጨት ለቀማም ይሁን
ዋርማ ይዤ ጅረት ስወርድ ጓደኛቼ እንደ ቀልድ 'አንቺዬ ማሳዘኗ' አንድ ቀን እኮ የሞቱት የዚች አባት ናቸው” እያሉ ሲያንሾካሽኩ እየሰማሁ ግራ ግብት ይለኝ ነበር። አባቴ ከሞተ በኋላ እዚያው አገር ቤት ከእናቴና ከእኅት ወንድሞቼ ጋር ቆየሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን የእናቴ ታላቅ እኅት ከአገር ቤት ወደ ከተማ ይዛኝ መጥታ ትምህርት ቤት አስገባችኝ ብላ ዝም ስላለች ያ በኀዘን ጉም ተሸፍኖ የቆየው ዐይኔ ቦግ ብሎ ወደ የወዲያነሽ ዐይኖች ተወረወረ፡፡እንባዋ እንደ አሸንዳ ጠፈጠፍ እየተንከባለለ በጉንጯ ላይ ተንኳለለ፡፡ ልብሴ ላይ የተንጠባጠበውን ዕንባዋን ደረቁ ሸሚዜ እንደ ግንቦት አፈር ጠጣው፡ የደቀነችውን ወሬ ለመጨረስ እንባዋን ካባበሰች በኋላ «አሁንም ቢሆን እነዚያ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ትዝ ይሉኛል። እነ የሻረግ፣ ዘነበች፡ አሚናት፡
ይመር፣ አያሌው፣ ገበያነሽ፣ ሰኢድ ኧረ ስንቱ ስንቱ... እክስቴ ከልጆቹ ሁሉ እኔን መርጣ የወሰደችኝ የረጋች ልጅ ነች፣ ደስ ትለኛለች» ብላ ነበር። ሁለት ሦስት ጊዜ ላግባ ባይ መጥቶ ሲጠይቅ ቆይ እስኪ ጥቂት ተምራ ነው ነፍስ ትወቅ» ብላ እምቢ አለቻቸው፡፡
እኔና እርሷ ብቻችንን ተቀምጠን በምናወራበት ጊዜ ግን፡ ያም የሸማኔ ልጅ ነው፣ ያኛው መናጢ ዘረ ድሃ ነው፣ የዚያኛውም እናት ዘር ማንዘሯ ሸክላ ሠሪ ነው የጠዳ የጨዋ ልጅ እስኪመጣ ሰጥ ብለሽ ትምርትሽን ተማሪ» ትለኝ ነበር፡፡ አክስቴ ከምላሷና ከንዝንኳ በስተቀር ሆዷ ባዶ ነው::ባልዋ አይዋ ዘለቀ አንድ ሲናገሩ ሁለትና ሦስት ነበር የምትመልስላቸው:: ችለው ችለው አንድ ቀን የተነሡ ለታ ግን ቀሽልደው ቀሽልደው ሲለቋት ውሃ ውስጥ የገባች አይጥ ትሆናለች። እሷ ታዲያ የሳቸውን እልክ በኔ ላይ ነበር የምትወጣው::
«አንቺ መድረሻ ቢስ ግንባረ ነጭ» ብላ ከጀመረች በርበሬ ሳታጥነኝና በጥርሷ ሳትበተብተኝ እንገላገልም፡፡ «አፈር ብይ! አፈር ያስበላሽ! ያባትሽን ቀን ይስጥሽ» ስትለኝ ግን አይመኙ ነገር ያስመኘኝ ነበር። ለጎ-ሐይቅ በሔድኩ በአራተኛው ዓመት አገር ቤት ወረርሽኝ ገባ ተባለና እናቴ በጠና ታመመች።ያኔውኑ ትምህርት ቤት በመዘጋቱ ካልሔድኩ ብዬ አገር አመስኩ፡፡ ቢሉኝ ቢፈጥሩኝ እዚያቹ ከናቴ
ጋር እሞታታለሁ እንጂ እይደረግም ብዬ
አስቸገርኩ፡፡ በማይረባው ነገር ሁሉ ካክስቴ ጋር መነታረኩ መሮኝ ስለ ነበር
ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከፊቷ ገለል ብዬ እፎይ ማለት ፈልጌ ነበር። ወሬ
አበዛሁብህ መሰል? ላሳጥርልህ፣ እናቴ ቡሄ በዋላ ልክ በሳምንቱ ሞተች። ያን
እለት የሆንኩትን አኳኋን ግን ባትሰማው ይሻላል። እናቴ ፀሐይነሽ አማረ ትባል ነበር። ከዘመዶቻችን ጋር ዕርባዋን አውጥቼ ትምህርት ቤት የተከፈተ
በሳምንቱ ከዚያቹ ከአክስቴ ጋር ወደ ከተማ ተመለስኩ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ወደ
አገር ቤት አልተመለስኩም» ብላ ጋደም አለች፡፡ ያ የቀድሞ ውበታዋም ርዝማኔውን ሊይዝ ጥቂት የቀረው የሴትነቷ ግርማ የሆነው ዞማ ጸጉሯ በአንገቷ ዙሪያ በተንተን ብሎ ተነሰነሰ። ድንገት
ቀና ብላ እግሯን ኮርምታ ተቀመጠች፡፡ «አልጨረስኩልህም እኮ» ብላ
ቀጠለች። በበኩሌ የሕይወቷ ምሬት አንገፍግፎኝ ነበር፡፡» ያክስቴ ባል ዘኃ
ነጋዴ ነበሩ። ከደሴ ዘኃ ያመጡና፣ ከሐይቅ ደግሞ አንጋሬና ቆዳ ይዘው
ይመለሳሉ። የኋላ ኋላ ግን ደሴ መሬት ገዝተው ቤት ስለሠሩና ንብረት ስላበጁ ሁላችንም ወደዚያው ሄድን። ደሴ ወይዘሮ ስሒን ትምህርት ቤት አምስተኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ያነዩ ገና ዐሥራ አራት ዓመቴ ነበር፡፡ አክስቴ ውሃ ቀጠነ፣ ጪስ በነነ፣ እያለች ስለምትነዛነዝ ይብስ እሳትና ጭድ ሆንን። እልህ ማብረጃ አረገችኝ፡፡ ስወጣም ስገባም ስድብና ዱላ ሆነ፡፡
ለጊዜውም ቢሆን ሌላ የሚያስጠጋኝና የምገባበት ዘመድ ስላልነበረኝ ያለችውን ብትል ታግሼ ዝም አልኩ፡፡ እንደ ምንም ብዬ ተፍጨርጭሬ ሰባተኛ ክፍል እንደ ገባሁ ከነከተቴው ሒጂልኝ! ውጪልኝ! ዐይንሽን ላፈር! ማለት አመጣች። ንግግሯ ሁሉ አንገሸገሸኝ፡፡ የዓመቱ ትምህርት ባሳር በመከራ ካለቀልኝ በኋላ ብሞትም ልሙት ብዩ ቆርጬ ተነሣሁ አንድ ቀን
ጎረቤታችን የነበሩ አንድ የጦር
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....እሑድ ከሰዓት በኋላ.….ስለ ለጎ ሐይቅ ከተማና አካባቢዋ ኣንድ ባንድ ካወራችልኝ በኋላ የሕሊናዋን ትዝታ ወደ ደሲ መልሳ ስለ በርበሬ ገንዳ ሙጋድ፣ ዳውዶ ገራዶ፣ ሆጤ፤ ሶሳ፣ አዘዋ ገደል ሰኞ ገበያ…. ነገረችኝ፡፡ «ቆየኝ ደግሞ ሥራዬን ጨርሼ ልምጣና አወራልሃለሁ» ብላ ካልጋው ጫፍ ላይ ሸርተት ብላ ሔደች፡፡ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ሥራዋን አጠናቃ ከተፍ አለች::ነጣ ያለ ቦላሌና ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሼ አልጋው ላይ በጀርባዬ ተንጋልዬ
የጋሻዬነህን ሥዕል አንጋጥጬ ስመለከት ደረሰች፡፡ ሲሠውረኝ አላየችብኝም፡፡
ትከሻዬ ሥር ጣል አድርጌ ተኛሁበት፡፡ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ በሆዴ
ላይ እጂን አሻግራ በመመርኮዝ ከደረቷ ዘንበል አለች፡፡ ትከሻዋ ላይ የነበረችው ባለ አረንጓዴ ጥለት ያንገት ልብስ ተንሸራተተችና የተዘረጋችውን እጅዋን ሸፈነቻት፡፡ ከደረቴ በታች የሆዴ አካባቢ በድንኳን ውስጥ ያላ ነጭ አግዳሚ መቀጫ መሰለ፡፡
ያን በሆዴ ላይ ዐልፎ አልጋው ላይ እንደ ካስማ የተተከለውን እጅዋን በቀኝ እጄ እያሻሽሁ ምናልባት ቅር ይላት ይሆን? በማለት ስፈራ ስቸር ከቆየሁ በኋላ የወዲያ፣ አንድ ነገር ብጠይቅሽ ቅር ይልሻል?» አልኳት፡፡ አሽቆልቁላ ዐይን ዐይኔን ትክ ብላ እያየች ምንስ ነገር ብትጠይቀኝ ምን ብዬ እቀየማለሁ? ስል ጠይቀኝ ልንገርህ? ብላ አቀማመጡዋን አመቻቸች።
ለሁለት ደቂቃ ያህል ውስጥ ውስጡን ሐሳቢን አንቀረቀብኩ፡፡ እንግዲህ
ያለችውን ትበል አልኩና «የወዲያ! ለምን አስታወስከኝ ኣትበይና፣ እናትና
አባትሽ ሲሞቱ የስንት ዓመት ልጅ ነበርሽ?» አልኳት። ፈገግታዋን የቅሬታ
ደም ስለ በረዘው ፊቷ ፈዞ የክረምት ዋዜማ መሰለ፡ ውስጥ ውስጡን ራሴን
«ጌታነህ! የተዳፈነ የኅዘን ረመጥ ጫርክ፣ ያንቀላፋ ኀዘን ቀሰቀስክ» ብዩ ወቀስኩ፡፡ ደቂቃዎች ሠገሩ። ትንሽ ፈነከነክ ብላ «ምነው ምን ነካሀና ኖረሀ ኖረህ ጠየቅኸኝ?» ብላ ፊቷን የትካዜ ዐመድ ነሰነሰችበት፡፡ ካኣሁን አሁን ትጀምራለች በማለት አሰፍስፌ ጠበቅሁ፡፡ ያን እንደ አተር እምቡጥ እበጥ ብሎ የቆየ የታች ከንፈሯን በላይኛው ውብ ጥርሷ ረመጠጠችው። አንድ ጊዜ
አፈትልኮ የተነገረን ሐሳብ መልሶ መዋጥ የማይቻል በመሆኑ ችሎታዩ ከዝምታ ሊያልፍ አልቻለም። እየር ስትስብና ስታስወጣ ከፍና ዝቅ የሚለውን
ደረቷን በመመልከት ላይ እንዳለ «አባቴ ሲሞት አንዲት ፍሬ ልጅ ነበርኩ
አሉ፡፡ ትንሽ ትንሽ እንደ ሕልም ትዝ ይለኛል፡፡ እናቴም አባትሽ ከልጆቹ
ሁሉ አንቺን ይወድሽ ነበር፡፡ ሳይንት እሚባል አገር ካሉት ዘመዶቹ መኻል
የሚወዳትን አክስቱን ስለምትመስዪ የእርሷ ነገር ሆነበትና 'የወዲያነሽ የወዲያ
ሰው ብሎ ስም አወጣልሽና የወዲያዬ የወዲያነሽ አልንሽ ብላ ነገረችኝ። ልጅ
ስለ ነበርኩ ሁሉንም ኣላስታውስም እንጂ አባቴ ብዙ ጊዜ ታሞና ማቆ ማቆ
ነው የሞተው። የሞተ ዕለት ሰዎች ሁሉ ሲያለቅሱ አይቼ እኔም ትንሽ
አልቅሻለሁ፡፡ ሞት ምን እንደሆነ ስለማላውቅ ሄዶ የሚመለስ እንጂ በዚያው የሚቀር አይመስለኝም ነበር፡፡ ሬሳውን በአልጋ ይዘው ከቤት ሲወጡ ምንም ስላልመሰለኝ ጉድሮዬን እያዘናፈልኩ ከመንደሩ ልጆች ጋር እቦርቅ ነበር፡፡
ታናሽ እኅቴ እማዋይሽ ክርስትና የተነሣች ዕለት መጥተው የነበሩት ቄሶች ራሱ የቀብሩም ዕለት መጥተው ስለነበር ለደስታ የመጡ እንጂ ለሌላ ነገር
የመጡ አልመሰለኝም። እያደር ግን ዋል አደር ስል ዕንጨት ለቀማም ይሁን
ዋርማ ይዤ ጅረት ስወርድ ጓደኛቼ እንደ ቀልድ 'አንቺዬ ማሳዘኗ' አንድ ቀን እኮ የሞቱት የዚች አባት ናቸው” እያሉ ሲያንሾካሽኩ እየሰማሁ ግራ ግብት ይለኝ ነበር። አባቴ ከሞተ በኋላ እዚያው አገር ቤት ከእናቴና ከእኅት ወንድሞቼ ጋር ቆየሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን የእናቴ ታላቅ እኅት ከአገር ቤት ወደ ከተማ ይዛኝ መጥታ ትምህርት ቤት አስገባችኝ ብላ ዝም ስላለች ያ በኀዘን ጉም ተሸፍኖ የቆየው ዐይኔ ቦግ ብሎ ወደ የወዲያነሽ ዐይኖች ተወረወረ፡፡እንባዋ እንደ አሸንዳ ጠፈጠፍ እየተንከባለለ በጉንጯ ላይ ተንኳለለ፡፡ ልብሴ ላይ የተንጠባጠበውን ዕንባዋን ደረቁ ሸሚዜ እንደ ግንቦት አፈር ጠጣው፡ የደቀነችውን ወሬ ለመጨረስ እንባዋን ካባበሰች በኋላ «አሁንም ቢሆን እነዚያ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ትዝ ይሉኛል። እነ የሻረግ፣ ዘነበች፡ አሚናት፡
ይመር፣ አያሌው፣ ገበያነሽ፣ ሰኢድ ኧረ ስንቱ ስንቱ... እክስቴ ከልጆቹ ሁሉ እኔን መርጣ የወሰደችኝ የረጋች ልጅ ነች፣ ደስ ትለኛለች» ብላ ነበር። ሁለት ሦስት ጊዜ ላግባ ባይ መጥቶ ሲጠይቅ ቆይ እስኪ ጥቂት ተምራ ነው ነፍስ ትወቅ» ብላ እምቢ አለቻቸው፡፡
እኔና እርሷ ብቻችንን ተቀምጠን በምናወራበት ጊዜ ግን፡ ያም የሸማኔ ልጅ ነው፣ ያኛው መናጢ ዘረ ድሃ ነው፣ የዚያኛውም እናት ዘር ማንዘሯ ሸክላ ሠሪ ነው የጠዳ የጨዋ ልጅ እስኪመጣ ሰጥ ብለሽ ትምርትሽን ተማሪ» ትለኝ ነበር፡፡ አክስቴ ከምላሷና ከንዝንኳ በስተቀር ሆዷ ባዶ ነው::ባልዋ አይዋ ዘለቀ አንድ ሲናገሩ ሁለትና ሦስት ነበር የምትመልስላቸው:: ችለው ችለው አንድ ቀን የተነሡ ለታ ግን ቀሽልደው ቀሽልደው ሲለቋት ውሃ ውስጥ የገባች አይጥ ትሆናለች። እሷ ታዲያ የሳቸውን እልክ በኔ ላይ ነበር የምትወጣው::
«አንቺ መድረሻ ቢስ ግንባረ ነጭ» ብላ ከጀመረች በርበሬ ሳታጥነኝና በጥርሷ ሳትበተብተኝ እንገላገልም፡፡ «አፈር ብይ! አፈር ያስበላሽ! ያባትሽን ቀን ይስጥሽ» ስትለኝ ግን አይመኙ ነገር ያስመኘኝ ነበር። ለጎ-ሐይቅ በሔድኩ በአራተኛው ዓመት አገር ቤት ወረርሽኝ ገባ ተባለና እናቴ በጠና ታመመች።ያኔውኑ ትምህርት ቤት በመዘጋቱ ካልሔድኩ ብዬ አገር አመስኩ፡፡ ቢሉኝ ቢፈጥሩኝ እዚያቹ ከናቴ
ጋር እሞታታለሁ እንጂ እይደረግም ብዬ
አስቸገርኩ፡፡ በማይረባው ነገር ሁሉ ካክስቴ ጋር መነታረኩ መሮኝ ስለ ነበር
ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከፊቷ ገለል ብዬ እፎይ ማለት ፈልጌ ነበር። ወሬ
አበዛሁብህ መሰል? ላሳጥርልህ፣ እናቴ ቡሄ በዋላ ልክ በሳምንቱ ሞተች። ያን
እለት የሆንኩትን አኳኋን ግን ባትሰማው ይሻላል። እናቴ ፀሐይነሽ አማረ ትባል ነበር። ከዘመዶቻችን ጋር ዕርባዋን አውጥቼ ትምህርት ቤት የተከፈተ
በሳምንቱ ከዚያቹ ከአክስቴ ጋር ወደ ከተማ ተመለስኩ፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ወደ
አገር ቤት አልተመለስኩም» ብላ ጋደም አለች፡፡ ያ የቀድሞ ውበታዋም ርዝማኔውን ሊይዝ ጥቂት የቀረው የሴትነቷ ግርማ የሆነው ዞማ ጸጉሯ በአንገቷ ዙሪያ በተንተን ብሎ ተነሰነሰ። ድንገት
ቀና ብላ እግሯን ኮርምታ ተቀመጠች፡፡ «አልጨረስኩልህም እኮ» ብላ
ቀጠለች። በበኩሌ የሕይወቷ ምሬት አንገፍግፎኝ ነበር፡፡» ያክስቴ ባል ዘኃ
ነጋዴ ነበሩ። ከደሴ ዘኃ ያመጡና፣ ከሐይቅ ደግሞ አንጋሬና ቆዳ ይዘው
ይመለሳሉ። የኋላ ኋላ ግን ደሴ መሬት ገዝተው ቤት ስለሠሩና ንብረት ስላበጁ ሁላችንም ወደዚያው ሄድን። ደሴ ወይዘሮ ስሒን ትምህርት ቤት አምስተኛ ክፍል ገባሁ፡፡ ያነዩ ገና ዐሥራ አራት ዓመቴ ነበር፡፡ አክስቴ ውሃ ቀጠነ፣ ጪስ በነነ፣ እያለች ስለምትነዛነዝ ይብስ እሳትና ጭድ ሆንን። እልህ ማብረጃ አረገችኝ፡፡ ስወጣም ስገባም ስድብና ዱላ ሆነ፡፡
ለጊዜውም ቢሆን ሌላ የሚያስጠጋኝና የምገባበት ዘመድ ስላልነበረኝ ያለችውን ብትል ታግሼ ዝም አልኩ፡፡ እንደ ምንም ብዬ ተፍጨርጭሬ ሰባተኛ ክፍል እንደ ገባሁ ከነከተቴው ሒጂልኝ! ውጪልኝ! ዐይንሽን ላፈር! ማለት አመጣች። ንግግሯ ሁሉ አንገሸገሸኝ፡፡ የዓመቱ ትምህርት ባሳር በመከራ ካለቀልኝ በኋላ ብሞትም ልሙት ብዩ ቆርጬ ተነሣሁ አንድ ቀን
ጎረቤታችን የነበሩ አንድ የጦር
👍7
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
በሐሰት ተገንብቶ በተለበጠ አካባቢ ሁሉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ተገንጥሉ ልዩ ትክክለኛ አካባቢ ለመፍጠር ከፍ ያለ ችግር ያጋጥመዋል።ሁሉም በየበኩሉ የየራሱን የኑሮ ማሳ እያዳበረ በሚያርስበትና በሚያዘምርበት
ትክክለኛ ዓላማና ግብ ማምራት እንጂ፣ ይኸ እንዲህ ነው፣ ያኛው እንዲያ
አካባቢ፣ የራስን ዶማ እና መሣሪያ ይዞ በመቀላቀል ቀስ በቀስ ወደሚመኙት
ነው እያሉ መጃጃል ወደፊት መራመድ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ ነው:: ልክ
ያልሆነው ነገር ሁሉ ወለል ብሎ ቢታየኝም በግል ስክበው የሰነበትኩት
አስተሳሰብ ለጊዜውም ቢሆን በአካባቢዬ አሮጌ ልማድ ተዋጠ።
ባለሁበት ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ተርፎታል፣ ሞልቶታል፣ እየተባለ ነገር ግን ዝቅ ብሎ መታየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለምና የአካባቢን አስተያየትና ግምት ለመለወጥ ሲባል የሚደረግ ልዩ ልዩ ጥረት አንድም ፈጽሞ መውደቂያ ወይም ለጊዜው ቀጥ ብሎ መቆሚያ ሊሆን ይችላል፡፡ ግላዊ ስምና ክብርን ለመጠበቅና ለማስከበር ሲባል የሚደረግ የስግብግብነት ውጣ ውረድ ሁሉ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ የሥቃይ ሸክም ነው::
በግል ሀብት ጥሪት ፍላጎት የቆሰለና የበለዘ ሕሊናን ለማንጻትና ለማዳን የሚደረግ ጥረት መሪርና አድካሚ ነው:: ከቤተሰቦቼ የሚደርስብኝን ትችትና የወጪ ገቢ ሐሜት ለመከላከል ያህል የሕሊናዬን ዓላማ ቅንጣት ታህል ችላ ብዪ ሕይወት ኣልባ ተራ ስሜን ለማዳን ስል አንዲት የተለየች የሐሳብና የተግባር ዘመቻ ጀመርኩ። ሌሎችን ለመምሰልና ላይ ላዩን እኩል ሆኜ ለመታየት ስል አንዲት ባገልግሎት ላይ ከዋለች አራት ዓመት ያህል ያለፋት ቮልስዋገን መኪና ከስንት የደላላ ንትርክ በኋላ ገዛሁ፡፡ በክፍያው ላይ እኔና ጉልላት ተረባረብንበት፡፡ የጠንቃቃ ሰው ንብረት ስለ ነበረች በየጊዜው በመሰናከል አላስቸገረችኝም፡፡
ኑሮዬን መለስ ብዬ እያየሁ «የሕይወት ቀላል ፍቺ ይህች ትሆን? ወይስ ራስን የማታለያ ስሕተት» እያልኩ ማሰብ አዲሱ ልማዱ ሆነ፡፡ መስሎ መታየትና በጉራ ተኮፍሶ መወጣጠርን ከዚህም ከዚያም ቀሠምኩ፡፡ አንዳንድ ቀን ያን መበስበሱ እየታወቀ ቀለም እንደተቀባ ግንድ ላይ ላዩን ያሽበረቀ አስመሳይ ኑሮዬን መለስ ብዬ ሳየው ጎምዛዛ ኀዘን ይስማኝና በረጅሙ እተክዛለሁ። በሳምንት አንድና ሁለት ቀን እያመሽሁ መግባትና ሳይበዛም
መጠጥ መጎንጨትን ኣዘወተርኩ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከጧቱ ሁለት ሰዓት የወጣሁ ጥምብዝ ብዬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ገባሁ።
የወዲያነሽ ያጋጠማትን ያልታሰበ ችግር ችላ «አይ ጌትዩ! ስንቱን ለፈለፍከው ! መንጋት አበይለው ነጋ» አለችኝ ሰክሬ በገባሁ ማግሥት አብረን ቁርስ ስንበላ፡፡ ከዚያ በመጥፎ ልማዳዊ እምነት ተበክሎ ካደገው ልቦናዩ ምን አስነዋሪ ነገር ወጥቶ ይሆን በማለት በጣም ሠጋሁ፡፡ ከጎኔ ተነሥታ በስተጀርባዬ ቆመች፡፡ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ሁሉ ፊት ለፊቴ ባለው የቁም ሳጥን መስታዋት እመለከት ነበር። እሷም ይህችኑ ብልሃቴን ደርሳበት ኖሮ በመስተዋቲቱ ውስጥ ስታየኝ ዐይን ለዐይን ተጋጨን። የያዝኩትን
የእንቁላል ጥብስ ለመጉረስ አፈን ከፈት ላደርግ ሣቄ አመለጠኝና ተንከተከትኩ፡፡ እጄን ስባ ጎረሰችብኝ፡፡ 'ጌትዬ” አለችኝ ጉርሻዩን ቀምታ የልቧን ካደረሰች በኋላ፡፡ «ይኸው ዛሬ አምስተኛህ መሆኑ ነው መሰል ካንተ አላውቅምና ለምኑም ለምኑም ቢሆን ጥሩ አይደለም። ጌታነህ ሰክሮ እንዲህ አለ መባል ደግሞ አንዳች የሚያህል ነውር ነው። በዚያ ላይ ውርደቱ? ቅሌቱ... ጌትዬ አፈር ስበላልህ! ባንዲት እንጨት ስሔድ አትጠጣ፡ መቼም
ይኸን ጉድህን ጋሼ ጉልላት ኣልሰማም እንጂ ቢሰማማ....» ብላ አዘኔታና
ምክሯን አደባልቃ ከነገረችኝ በኋላ የተዳፈረችኝ ስለ መሰላት ሳይታወቃት
ትከሻዬን በግንባሯ ጠረግ ጠረግ እድርጋ ልትሸሽ ስትል እጅዋን ይዤ
አስቀረኋት፡፡
«ለመሆኑ ክፉ ነገር ተናገርኩ እንዴ? ሆድ ያባውን... የሚሉት ነገር ነበረበት?... አልኳት።
«የተናገርከው ሁሉ ምኑም አልገባኝ። እነዚያኑ ቤተሰቦችህን ስትሰድብና ስታጥላላ ነው ያደርከው:: እኔንም አይዞሽ በርቺ ድሉ ያንቺ ነው፤ ያባትሽ ስም አሸናፊ ነው እንቺም አሸናፊ ትሆኛለሽ እያልክ
ስታጫውተኝ አመሽህ» ብላ እጅዋን ነጥቃኝ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
የገዛ ስሕተቴን ለማስተባበል ሳይሆን ለማመኻንት ያህል ከጓዳ መለስ
እንዳለች «ትላንትም በል በል ብለው፣ አጠጥተውኝ ነው እንጂ ከእንግዲህ
ወዲህ መጠጥ በረበት ኣልዞርም» አልኳትና ወደ ሥራዬ ሄድኩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሌሊቱ አብዛኛውን ክፍል በሐሳብ ስገላበጥ አሳለፍኩት፡፡ እሑድ ጧት ከቁርስ በኋላ ሽር አልኩ። ሰበሰቡ ላይ ቆም ብዬ የወዲያነሽን ጠራኋት።
ከወደ ውስጥ ከተፍ አለች፡፡ የምትለውን ለመስማት ያህል 'አይቆርጡን አይፈልጡን ነይ እስኪ ወላጆቼ ቤት ይዤሽ ልሂድ? እኔ እያለሁ ምንም
እትሆኚ» አልኳት፡፡
ከልቤ ስለ መሰላት ክው ብላ ደነገጠች፡፡ «እንዲህ ንገረኝና ይለይልኝ
እንጂ! እጄን ይዘህ አስገድለኛ! እንኳንስ ካንተ ጋር አብሬ እዚያች ቤት
ገብቼላቸውና መንገድ ላይ ያዩን ይሆን እያልኩ አካላቴ ይበጠቃል። ምን
ቅብጥ ልጄ! ይልቅስ ሂድ ይቅናህ!» ብላ በእርሷ አስተሳሰብ የልቧን ተናግሬ
እንዳበቃች መንገድ ገባሁ፡፡ ጠምዛዛው መንገድ ከዐይኗ እስከ ሰወረኝ ድረስ
የአጥር ግቢውን በር ተደግፋ በዐይኖቿ ሸንችኝ፡፡ መኪናዬን ከቀበና ድልድይ
በላይ አቁሜ በእግር ቀጠልኩ። የወላጆቼን ቤት ከረገጥኩ ሦስት ወር ያህል አልፎኝ ስለ ነበር በዱሮው ዘበኛ በአቶ በየነ ምትክ ሌላ ሰው ተቀጥረዋል።
አጠር ብለው ከወደ ዐይናቸው ላም ያሉ ጸጉረ ገብስማ ሽማግሌ ናቸው::
አያውቁኝም። ለመግባት ፍቃድ ጠየቅሁ። ደረታቸውን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥተው
ማንን ነው የምትፈልገው? ጌቶችና አሜቴ እንደሁ ቤተስኪያን ሊስሙ እንደ
ኤዱ አልተመለሱም፡፡ ቆየት ብለህ ተመልሰሀ ናና ነግሬልህ ትገባለህ» ብለው ፊታቸውን አዙረው ችላ አሉኝ፡፡ ቸልታቸው ስላበሳጨኝ ልጃቸውስ የለችም
እንዴ? እሷም ካለች ያው ነው» ብዬ ጠየቅኋቸው፡፡ በጥፊ የመታኋቸው ያህል
ብው ብለው ተናደዱ፡፡ «እንዴ! እንዴ! መች አበድኩና! አንተ ስለ እኔ
እንጀራ ምንቸገረህ! የዋዛ ቤት መስሎሃል! እዚች ቦታም አያውሉኝ!» አሉና ነገሩኝ፡፡ ቀባጥሬም ሆነ ማንነቴን አስረድቼ መግባት ስላልፈለግሁ ደጅ ደጁን እያልኩ ለመቆየት ወሰንኩ፡፡ በዚያው አካባቢ መለስ ቀለስ ስል የውብነሽ ባዘቶ የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሳ ስትመጣ አየኋት።አመጣጧ በእኔው ኣቅጣጫ ስለ ነበር ቆሜ ጠበቅኋት። ከሩቅ የጀመረው ፈገግታዋ አጠገቤ ስትደርስ ተራውን ለውብ ጥርሶቿ ለቀቀ፡፡ ከጋቢው ሥር እጅዋን ብቅ አድርጋ ጨበጠችኝ፡፡ ስሜቷን ለመሸንገል ያህል ሳምኳት፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ሽማግሌው ኣጠገብ ደረስን፡፡ ቀና ብለው ከእግር እስከ ራሴ አዩኝ። ይኸ ደግሞ የማን ነው? በሚል አስተያየት እየገረመሙኝ አልፈናቸው ገባን፡፡
በምድረ ግቢው ያሉት አበቦችና አትክልቶች በጣም ያማሩ መሰለኝ፡፡
ከየውብነሽ ጋር እያወራሁ ዐይኖቼ ካትክልቶቸ ላይ አልተነቀሉም፡፡ እነዚያ
ምን ጊዜም ሌላ መሄጂያና መግቢያ የሌላቸው የሚመስሉት ነባር ሠራተኞች
ናፍቆትን በሚገልጽ ፈገግታ እጅ ነሡኝ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ዛሬ የጌቶች
ልጅ ከየት መጡ?” እንደሚሉ ታወቀኝ፡፡ አንደኛዋ ሠራተኛ እማማ ወለተሩፋኤልማ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ እኔ ግን ገና ከልጅነቴ ጀምሮ አልወዳቸውም ነበር፡፡ ኣብሮ ከመኖር ብዛት የተነሣ
እናትና አባቴ እንደ "ገረድ አያዩዋቸውም፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
በሐሰት ተገንብቶ በተለበጠ አካባቢ ሁሉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ተገንጥሉ ልዩ ትክክለኛ አካባቢ ለመፍጠር ከፍ ያለ ችግር ያጋጥመዋል።ሁሉም በየበኩሉ የየራሱን የኑሮ ማሳ እያዳበረ በሚያርስበትና በሚያዘምርበት
ትክክለኛ ዓላማና ግብ ማምራት እንጂ፣ ይኸ እንዲህ ነው፣ ያኛው እንዲያ
አካባቢ፣ የራስን ዶማ እና መሣሪያ ይዞ በመቀላቀል ቀስ በቀስ ወደሚመኙት
ነው እያሉ መጃጃል ወደፊት መራመድ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ ነው:: ልክ
ያልሆነው ነገር ሁሉ ወለል ብሎ ቢታየኝም በግል ስክበው የሰነበትኩት
አስተሳሰብ ለጊዜውም ቢሆን በአካባቢዬ አሮጌ ልማድ ተዋጠ።
ባለሁበት ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ተርፎታል፣ ሞልቶታል፣ እየተባለ ነገር ግን ዝቅ ብሎ መታየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለምና የአካባቢን አስተያየትና ግምት ለመለወጥ ሲባል የሚደረግ ልዩ ልዩ ጥረት አንድም ፈጽሞ መውደቂያ ወይም ለጊዜው ቀጥ ብሎ መቆሚያ ሊሆን ይችላል፡፡ ግላዊ ስምና ክብርን ለመጠበቅና ለማስከበር ሲባል የሚደረግ የስግብግብነት ውጣ ውረድ ሁሉ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ የሥቃይ ሸክም ነው::
በግል ሀብት ጥሪት ፍላጎት የቆሰለና የበለዘ ሕሊናን ለማንጻትና ለማዳን የሚደረግ ጥረት መሪርና አድካሚ ነው:: ከቤተሰቦቼ የሚደርስብኝን ትችትና የወጪ ገቢ ሐሜት ለመከላከል ያህል የሕሊናዬን ዓላማ ቅንጣት ታህል ችላ ብዪ ሕይወት ኣልባ ተራ ስሜን ለማዳን ስል አንዲት የተለየች የሐሳብና የተግባር ዘመቻ ጀመርኩ። ሌሎችን ለመምሰልና ላይ ላዩን እኩል ሆኜ ለመታየት ስል አንዲት ባገልግሎት ላይ ከዋለች አራት ዓመት ያህል ያለፋት ቮልስዋገን መኪና ከስንት የደላላ ንትርክ በኋላ ገዛሁ፡፡ በክፍያው ላይ እኔና ጉልላት ተረባረብንበት፡፡ የጠንቃቃ ሰው ንብረት ስለ ነበረች በየጊዜው በመሰናከል አላስቸገረችኝም፡፡
ኑሮዬን መለስ ብዬ እያየሁ «የሕይወት ቀላል ፍቺ ይህች ትሆን? ወይስ ራስን የማታለያ ስሕተት» እያልኩ ማሰብ አዲሱ ልማዱ ሆነ፡፡ መስሎ መታየትና በጉራ ተኮፍሶ መወጣጠርን ከዚህም ከዚያም ቀሠምኩ፡፡ አንዳንድ ቀን ያን መበስበሱ እየታወቀ ቀለም እንደተቀባ ግንድ ላይ ላዩን ያሽበረቀ አስመሳይ ኑሮዬን መለስ ብዬ ሳየው ጎምዛዛ ኀዘን ይስማኝና በረጅሙ እተክዛለሁ። በሳምንት አንድና ሁለት ቀን እያመሽሁ መግባትና ሳይበዛም
መጠጥ መጎንጨትን ኣዘወተርኩ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከጧቱ ሁለት ሰዓት የወጣሁ ጥምብዝ ብዬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ገባሁ።
የወዲያነሽ ያጋጠማትን ያልታሰበ ችግር ችላ «አይ ጌትዩ! ስንቱን ለፈለፍከው ! መንጋት አበይለው ነጋ» አለችኝ ሰክሬ በገባሁ ማግሥት አብረን ቁርስ ስንበላ፡፡ ከዚያ በመጥፎ ልማዳዊ እምነት ተበክሎ ካደገው ልቦናዩ ምን አስነዋሪ ነገር ወጥቶ ይሆን በማለት በጣም ሠጋሁ፡፡ ከጎኔ ተነሥታ በስተጀርባዬ ቆመች፡፡ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ሁሉ ፊት ለፊቴ ባለው የቁም ሳጥን መስታዋት እመለከት ነበር። እሷም ይህችኑ ብልሃቴን ደርሳበት ኖሮ በመስተዋቲቱ ውስጥ ስታየኝ ዐይን ለዐይን ተጋጨን። የያዝኩትን
የእንቁላል ጥብስ ለመጉረስ አፈን ከፈት ላደርግ ሣቄ አመለጠኝና ተንከተከትኩ፡፡ እጄን ስባ ጎረሰችብኝ፡፡ 'ጌትዬ” አለችኝ ጉርሻዩን ቀምታ የልቧን ካደረሰች በኋላ፡፡ «ይኸው ዛሬ አምስተኛህ መሆኑ ነው መሰል ካንተ አላውቅምና ለምኑም ለምኑም ቢሆን ጥሩ አይደለም። ጌታነህ ሰክሮ እንዲህ አለ መባል ደግሞ አንዳች የሚያህል ነውር ነው። በዚያ ላይ ውርደቱ? ቅሌቱ... ጌትዬ አፈር ስበላልህ! ባንዲት እንጨት ስሔድ አትጠጣ፡ መቼም
ይኸን ጉድህን ጋሼ ጉልላት ኣልሰማም እንጂ ቢሰማማ....» ብላ አዘኔታና
ምክሯን አደባልቃ ከነገረችኝ በኋላ የተዳፈረችኝ ስለ መሰላት ሳይታወቃት
ትከሻዬን በግንባሯ ጠረግ ጠረግ እድርጋ ልትሸሽ ስትል እጅዋን ይዤ
አስቀረኋት፡፡
«ለመሆኑ ክፉ ነገር ተናገርኩ እንዴ? ሆድ ያባውን... የሚሉት ነገር ነበረበት?... አልኳት።
«የተናገርከው ሁሉ ምኑም አልገባኝ። እነዚያኑ ቤተሰቦችህን ስትሰድብና ስታጥላላ ነው ያደርከው:: እኔንም አይዞሽ በርቺ ድሉ ያንቺ ነው፤ ያባትሽ ስም አሸናፊ ነው እንቺም አሸናፊ ትሆኛለሽ እያልክ
ስታጫውተኝ አመሽህ» ብላ እጅዋን ነጥቃኝ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
የገዛ ስሕተቴን ለማስተባበል ሳይሆን ለማመኻንት ያህል ከጓዳ መለስ
እንዳለች «ትላንትም በል በል ብለው፣ አጠጥተውኝ ነው እንጂ ከእንግዲህ
ወዲህ መጠጥ በረበት ኣልዞርም» አልኳትና ወደ ሥራዬ ሄድኩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሌሊቱ አብዛኛውን ክፍል በሐሳብ ስገላበጥ አሳለፍኩት፡፡ እሑድ ጧት ከቁርስ በኋላ ሽር አልኩ። ሰበሰቡ ላይ ቆም ብዬ የወዲያነሽን ጠራኋት።
ከወደ ውስጥ ከተፍ አለች፡፡ የምትለውን ለመስማት ያህል 'አይቆርጡን አይፈልጡን ነይ እስኪ ወላጆቼ ቤት ይዤሽ ልሂድ? እኔ እያለሁ ምንም
እትሆኚ» አልኳት፡፡
ከልቤ ስለ መሰላት ክው ብላ ደነገጠች፡፡ «እንዲህ ንገረኝና ይለይልኝ
እንጂ! እጄን ይዘህ አስገድለኛ! እንኳንስ ካንተ ጋር አብሬ እዚያች ቤት
ገብቼላቸውና መንገድ ላይ ያዩን ይሆን እያልኩ አካላቴ ይበጠቃል። ምን
ቅብጥ ልጄ! ይልቅስ ሂድ ይቅናህ!» ብላ በእርሷ አስተሳሰብ የልቧን ተናግሬ
እንዳበቃች መንገድ ገባሁ፡፡ ጠምዛዛው መንገድ ከዐይኗ እስከ ሰወረኝ ድረስ
የአጥር ግቢውን በር ተደግፋ በዐይኖቿ ሸንችኝ፡፡ መኪናዬን ከቀበና ድልድይ
በላይ አቁሜ በእግር ቀጠልኩ። የወላጆቼን ቤት ከረገጥኩ ሦስት ወር ያህል አልፎኝ ስለ ነበር በዱሮው ዘበኛ በአቶ በየነ ምትክ ሌላ ሰው ተቀጥረዋል።
አጠር ብለው ከወደ ዐይናቸው ላም ያሉ ጸጉረ ገብስማ ሽማግሌ ናቸው::
አያውቁኝም። ለመግባት ፍቃድ ጠየቅሁ። ደረታቸውን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥተው
ማንን ነው የምትፈልገው? ጌቶችና አሜቴ እንደሁ ቤተስኪያን ሊስሙ እንደ
ኤዱ አልተመለሱም፡፡ ቆየት ብለህ ተመልሰሀ ናና ነግሬልህ ትገባለህ» ብለው ፊታቸውን አዙረው ችላ አሉኝ፡፡ ቸልታቸው ስላበሳጨኝ ልጃቸውስ የለችም
እንዴ? እሷም ካለች ያው ነው» ብዬ ጠየቅኋቸው፡፡ በጥፊ የመታኋቸው ያህል
ብው ብለው ተናደዱ፡፡ «እንዴ! እንዴ! መች አበድኩና! አንተ ስለ እኔ
እንጀራ ምንቸገረህ! የዋዛ ቤት መስሎሃል! እዚች ቦታም አያውሉኝ!» አሉና ነገሩኝ፡፡ ቀባጥሬም ሆነ ማንነቴን አስረድቼ መግባት ስላልፈለግሁ ደጅ ደጁን እያልኩ ለመቆየት ወሰንኩ፡፡ በዚያው አካባቢ መለስ ቀለስ ስል የውብነሽ ባዘቶ የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሳ ስትመጣ አየኋት።አመጣጧ በእኔው ኣቅጣጫ ስለ ነበር ቆሜ ጠበቅኋት። ከሩቅ የጀመረው ፈገግታዋ አጠገቤ ስትደርስ ተራውን ለውብ ጥርሶቿ ለቀቀ፡፡ ከጋቢው ሥር እጅዋን ብቅ አድርጋ ጨበጠችኝ፡፡ ስሜቷን ለመሸንገል ያህል ሳምኳት፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ሽማግሌው ኣጠገብ ደረስን፡፡ ቀና ብለው ከእግር እስከ ራሴ አዩኝ። ይኸ ደግሞ የማን ነው? በሚል አስተያየት እየገረመሙኝ አልፈናቸው ገባን፡፡
በምድረ ግቢው ያሉት አበቦችና አትክልቶች በጣም ያማሩ መሰለኝ፡፡
ከየውብነሽ ጋር እያወራሁ ዐይኖቼ ካትክልቶቸ ላይ አልተነቀሉም፡፡ እነዚያ
ምን ጊዜም ሌላ መሄጂያና መግቢያ የሌላቸው የሚመስሉት ነባር ሠራተኞች
ናፍቆትን በሚገልጽ ፈገግታ እጅ ነሡኝ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ዛሬ የጌቶች
ልጅ ከየት መጡ?” እንደሚሉ ታወቀኝ፡፡ አንደኛዋ ሠራተኛ እማማ ወለተሩፋኤልማ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ እኔ ግን ገና ከልጅነቴ ጀምሮ አልወዳቸውም ነበር፡፡ ኣብሮ ከመኖር ብዛት የተነሣ
እናትና አባቴ እንደ "ገረድ አያዩዋቸውም፡፡
👍4
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
እናቴም የአባቴን አኳኋንና ለዘብተኛ አነጋገር በመከተል እንደ ወትሮዋ አልተቆጣችኝም
ከየውብነሽ ጋር መገናኘቴን ቀጠልኩ። አባቴ ስለ እኔ ያለውን አስተያየት እምብዛም እንዳልለወጠው አጣራሁ፡፡ እናቴም የእኔን ደጅ ደጅ ማየት ችላ እንዳለችውና እንኳን ከዚያች ከመናጢ ገረድ ጋር አብሮ ያልታየና ስማችንን ያላስጠፋው እንጂ የኋላ ኋላ መመለሱና ልብ መግዛቱ አይቀርም፡፡ እኔም ለጊዜው ንድድ ያለኝ ከገረድ ጋር መዋልና መልከስከሱ ነበር፣ ሌላ ሌላውስ ግድ የለም” ማለቷን የዋህ ተመስዩ ከየውብነሽ ሰማሁ፡፡
ያም ሆነ ይህ አንድ ቀን የእኔንና የየወዲያነሽን ጉዳይ ይፋ ለማውጣት ቆርጬ በምነሣበት ጊዜ ንትርክና ከባድ የቤተሰብ ውዝግብ እንደሚያጋጥመኝ በእርግጠኝነት ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ካለፈ አገደም ከሥራ መልስ በምሳ ሰዓት ወደ ወላጆቼ ቤት እየሄድኩ የሻከረ ሆዳቸውንና
አስተያየታቸውን ደረጃ በደረጃ ለመለወጥ ጥሩ ጥረት አደረግሁ፡፡ ተደጋጋሚ
ሙከራዩ ትንሽ የለውጥ ፍሬ አሳየ፡፡ በተለይም ከእናቴ ጋር የማደርገው ወሬና
ጨዋታ ሁሉ አስደሳች ቅርርብ ፈጠረ፡፡ ትንሽም ፊቷ በኀዘን የሚጠወልግና
የጠራራ ቅጠል የምትመስለው ደህና እደሪ ብዬ ለመሄድ በምነሣበት ጊዜ
ነበር።
አንድ ቀን ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከየውብነሽ ጋር መኝታ ቤቷ ውስጥ
ተቀምጠን ሞቅ ደመቅ ያለ መሬ ስናወራ «አንተ ጌታነህ» አለችኝ፡፡ ዐይኖቿ
የትዝታዋን ክብደት ለማስረዳት እየቦዙ ያነዩ ዱሮ ከዚያች ከገረዳችን ጋር
እንዲያ ስትሆን አባባ ያየኛል፣ ይሰማብኛል ብለሀ አልፈራህም?» ብላ
ታላቅነቴን በማክበር የኃፍረት ሣቅ ሣቀች። ምናልባት አንዳንድ ያልሰማሁትን
ነገር ታሰማኝ ይሆናል በማለት ልበ ግልጽ
ተመስዩ «እንዳልታይና እንዳይሰማብኝ ያልሠራሁትና ያልፈጸምኩት ዘድ አልነበረም። አንቺንም በጣም እፈራሽና እጠራጠርሽ ነበር» አልኩና አልጋዋ ላይ ጣል ያደረገችውን የሰነበተ ጋዜጣ ማገላበጥ ጀመርኩ። አንገቷን ወደ ቀኝ ሰበር አድርጋ የማገላብጠውን
ጋዜጣ እየተመለከተች ግን እኮ እያደር እንዳፈቀርካትና ከወዲያ ወዲህ
እየተመላለሰች በምትሠራበት ጊዜ ዐይኖችህ አብረዋት እንደሚዋትቱ ኣሳምሬ ዐውቅ ነበር፡፡ ከእንጀራ አቅም እንኳ ሌላ ሰው ሲያቀርብልህ ደስ አይልህም ነበር። እሷም የዋዛ ሾላካ አልነበረችም ! ኋላማ ልናባርራት አቅራቢያ
አረማመዷና አነጋገሯ፣ ጸጉር አሠራሯና አለባበሷ ሁሉ በጣም ተሻሽሉ ነበር፡፡
እኔ ከሁሉም ከሁሉም የማይረሳኝ ጠባይዋና ሲያዝዋት እሺ ባይነቷ ነው፡፡ ምን ይሆናል፣ ያ መሳይ መልክ ያለ ቦታው ቀረ፡፡ እሷ የተማረች ሆና ውጪ
ውጪውን ብናገኛት ኖሮ... እኔ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ስለ እሷ አንዳችም ወሬ
ሰምቼ አላውቅም» ብላ አጠናቀቀች። የወሬ ከረጢቷን መፍታቷ ስለ ታወቀኝ
ለጊዜው ውስጣዊ ብስጭቴን ኣፍኜ ባናነሣው ይሻላል ያለፈው አልፏል እንጂ
ብሳሳትም ባልሳሳትም ከዚህ ቤት ስታባርሯት እርጉዝ ነበረች። ቀስ ብላችሁ
ሹክ ብትሉኝ ኖሮ እንደምንም አንዱ ጋ አስጠጋትና ትወልድ ነበር፡፡
ይኸንዬ እኔን አባብዬ” ሲል አንቺን ደግሞ ”እቴቴ' እቴ ሸንኮሬ 'እት -አይገኝ” ይልሽ ነበር» አልኳት፡፡ የአሁኑን የ'ወዲያነሽን ሕይወትና ኑሮ የማታውቀዋ እኅቴ ከሁሉም ከሁሉም በጣም የሚያሳዝነኝ» ብላ ቀጠለች፣
«ያነዪ አንተ ወደ ሥራ ወጣ ከማለትu እማዬ በአባባ ከዘራ ታፋ ታፋዋን'
ጀርባ ጀርባዋን ስትደበድባት ኩርምት ብላ ስትደበደብ የወረደባት የዱላ መዓት ነው፡፡ በመጨረሻ የተሰነዘረው ዱላ መኻል እናቷ ላይ በማረፉ ደሟ በጸጉሯ ውስጥ እየተንጀረጀረ ትከሻዋ ላይ ተንጠፈጠፈ፡፡ ነፍስ ይዟትም ይሁን ያሰበችውን እንጃ ከዘራውን ይዛ እለቅም በማለቷ እኔም እናቴን የተዳፈረችብኝና ግብግብ የምትገጥማት ስለመሰለኝ ሁለት ጊዜ በጥፊ አላስኳት።
«እሷ ግን ቀና ብላ አይታ፣ አንቺም? አንቺም? ጨክነሽ ትመቺኝ የውብነሽ? ኣይ ድኃ መሆን!” ያለችኝ ዛሬም አንጀት አንጀቴን ይበላኛል፡፡»
«እሷ ግን በጣም የተንገበገበችውና ያለቀሰችው ከቤት በመባረሯና
በመደብደቧ ሳይሆን እንተን ሳትሰናበትሀና ሳታይህ በመሔዷ ነበር። ከሥራ ስትመለስ መንገድ ላይ ጠብቃ እንዳታግባባሀና በሴት እንባዋ እንዳታታልልህ ከዚህ አካባቢ ያባረርናት በዘበኛ ነበር» ብላ ያን ዚያ ቀደም አሳርሮ
ያከሰለኝን መራራ ነገር እንደገና ጋተችኝ፡፡ የየወዲያነሽ መከራና እንግልት
ሁሉ ከተቀበረበት የትዝብት መቃብር ወጥቶ ነጭ ዓፅሙ ፊት ለፊቴ ተገተረ፡፡ ሌላ ተጨማሪ ነገር በመስማት አንጎሌን ማጥመልመል ስላልፈለግሁ
«ነገ አራት ሰዓት ላይ ዕጓለ ማውታ ስለምሔድ አብረን እንሂድ። ከዚያ በኋላ
ደግሞ ሌላ የማማክርሽ ጉዳይ ስላለ ቀደም ብለሽ ቀበና ድልድይ አጠገብ
ጠብቂኝ ብያት ወጣሁ፡፡
በማግሥቱ እሑድ እኅቴና ባለቤቴ ዕጓለ ማውታ እንዳይገናኙብኝ፡ የወዲያነሽን «እንግዳ ይዤ እመጣለሁና ተዘጋጅተሽ እንድትጠብቂኝ፡ ከዚያ በኋላ እንሔዳለን» ብያት ከቤት ወጣሁ፡፡ መኪና መግዛቴን መላ ቤተሰቦቼ ስላልሰሙ የውብነሽ የምትጠብቀኝ በእግር እንጂ በመኪና ይመጣል ብላ አልነበረም፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ዘግየት ብዬ ቀጠሮእችን ቦታ ስደርስ የውብነሽ ተረከዘ ሹል ጫማ አድርጋ ከጉልበቷ ትንሽ ከፍ ያለ ቀለመ ብዙ የፈረንጅ ቅድ ቀሚስና ነጭ ሸሚዝ ለብሳ ቡናማ ኮረጆዋን አንግታ ድልድዩ አካባቢ ስትጠብቀኝ አገኘኋት። መኪና አጠገቧ ደርሳ በመቆሟ ባለ መኪናውም እኔ መሆኔን ባለማወቋ ፊቷን በቁጣ ከሰከሰች፡፡ እንዳንድ የጎዳና ሴቶች
ለመግደርደር ሲሉ የሚያሳዩት አኳኋን ትዝ አለኝና የየውብነሽ አድራጎት አሣቀኝ፡፡ ወዲያው ወጣ ብዬ ወደ እርሷ ተራመድኩ። ከመኪና ወጥቶ ወደ
እርሷ የሚራመደው ሰው ታላቅ ወንድሟ መሆኑን ስታውቅ የአድናቆት ሣቅ
ሣቀች፡፡
«መኪና ገዛሁ እንዳትለኝ አለችኝ፡፡ «አዎ ገዛሁ እኔም ወጉ ይድረሰኝ ብዬ ገና ሁለተኛ ወሯን መያዟ ነው» አልኩና እየተሣሣቅን ተጨባበጥን፡፡
«የውቤ፣ ይቺንም ታድያ ቤተሰብ እንዳይሰማ፣ እንድ ቀን ሁሉንም ነገር
አጠራቅሜ አቀርበዋለሁ፡፡» «ሌላ ደግሞ ምን የሚነገር አለህ?» ብላ አየችኝ፡፡
«እኔ ገና ብዙ የሚነገር ነገር አለኝ» ብያት መኪና ውስጥ ገብተን መንገድ
ቀጠልን፡፡ በአሥራ አምስት ደቂቃ ውስጥ አግድመት ቁልቁለቱን ጨርሰን
ሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ደረስን፡፡ ለምለሙ መስክ ላይ ትላልቅና ትናንሽ
ልጆች እንደ ጥሬ ፈስሰው ልዩ ልዩ ጨዋታዎች ይጫወታሉ። ከትንንሾቹ
ልጆች መኻል አንድ የግራ ዐይኑ የጠፋችና በዐይን አር የተጨማለቀች
ሰማያዊ ቁምጣና ትከሻው ላይ የተጣፈች እሷኑ መሰል ኮት የለበሰ ልጅ
በሩጫ መጥቶ ጨበጠኝ፡፡ የጋሻዬነህ ጓደኛ ነው:: ከኪሴ ከረሜላ ኣውጥቼ ሰጠሁት። የውብነሽ በድንጋጤ አፏን ከፍታ «ምነው ምን ሆነ? ዐይኑን ምን ነካው? ደኅና አልነበረም እንዴ !?» አለችኝ፡፡
«ይህ እኮ ያ ከዚህ ቀደም ያየሽው የጓደኛዬ ልጅ አይደለም፣ ይኸ ጓደኛዉ ነው:: አሁን ሮጦ ይጠራልናል» አልኩና የደነገጠውን ስሜቷን በደስታ
አደስኩት:: ከረሜላውን ልጦ ጎረሰና ተለይቶን ሔደ። እምብዛም ሳይቆይ
ጋሻነህን ይዞት መጣ፡፡ አንዲት በጣም የጠወለገች ነጭ አበባ ይዞ ነበረ።
እጆቼን ከብብቱ ሥር አስገብቼ በማንሣት ጉንጮቹን ስስም ሁሉም ነገር
ጥሉኝ ጠፋ፡፡ የውብነሽ ቀበል ብላ አገላብጣ ሳመችው:: ቀድሞውንም የሙት ልጅ ነው ብዬ ነግሬያት ስለ ነበር በርኅራኄ ተመለከተችው:: አላስችል ስላላት ዕንባ ተናነቃት። መሐረቧን አውጥቃ ዐይኖቿን አበሰች። «ለመሆኑ ያባቱ ዘመዶች እየመጡ ይጠይቁታል እንዴ?» አለችኝ፡፡ ልጅ ያለው መሆኑን የሰማ አንድም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
እናቴም የአባቴን አኳኋንና ለዘብተኛ አነጋገር በመከተል እንደ ወትሮዋ አልተቆጣችኝም
ከየውብነሽ ጋር መገናኘቴን ቀጠልኩ። አባቴ ስለ እኔ ያለውን አስተያየት እምብዛም እንዳልለወጠው አጣራሁ፡፡ እናቴም የእኔን ደጅ ደጅ ማየት ችላ እንዳለችውና እንኳን ከዚያች ከመናጢ ገረድ ጋር አብሮ ያልታየና ስማችንን ያላስጠፋው እንጂ የኋላ ኋላ መመለሱና ልብ መግዛቱ አይቀርም፡፡ እኔም ለጊዜው ንድድ ያለኝ ከገረድ ጋር መዋልና መልከስከሱ ነበር፣ ሌላ ሌላውስ ግድ የለም” ማለቷን የዋህ ተመስዩ ከየውብነሽ ሰማሁ፡፡
ያም ሆነ ይህ አንድ ቀን የእኔንና የየወዲያነሽን ጉዳይ ይፋ ለማውጣት ቆርጬ በምነሣበት ጊዜ ንትርክና ከባድ የቤተሰብ ውዝግብ እንደሚያጋጥመኝ በእርግጠኝነት ወለል ብሎ ታየኝ፡፡ ካለፈ አገደም ከሥራ መልስ በምሳ ሰዓት ወደ ወላጆቼ ቤት እየሄድኩ የሻከረ ሆዳቸውንና
አስተያየታቸውን ደረጃ በደረጃ ለመለወጥ ጥሩ ጥረት አደረግሁ፡፡ ተደጋጋሚ
ሙከራዩ ትንሽ የለውጥ ፍሬ አሳየ፡፡ በተለይም ከእናቴ ጋር የማደርገው ወሬና
ጨዋታ ሁሉ አስደሳች ቅርርብ ፈጠረ፡፡ ትንሽም ፊቷ በኀዘን የሚጠወልግና
የጠራራ ቅጠል የምትመስለው ደህና እደሪ ብዬ ለመሄድ በምነሣበት ጊዜ
ነበር።
አንድ ቀን ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከየውብነሽ ጋር መኝታ ቤቷ ውስጥ
ተቀምጠን ሞቅ ደመቅ ያለ መሬ ስናወራ «አንተ ጌታነህ» አለችኝ፡፡ ዐይኖቿ
የትዝታዋን ክብደት ለማስረዳት እየቦዙ ያነዩ ዱሮ ከዚያች ከገረዳችን ጋር
እንዲያ ስትሆን አባባ ያየኛል፣ ይሰማብኛል ብለሀ አልፈራህም?» ብላ
ታላቅነቴን በማክበር የኃፍረት ሣቅ ሣቀች። ምናልባት አንዳንድ ያልሰማሁትን
ነገር ታሰማኝ ይሆናል በማለት ልበ ግልጽ
ተመስዩ «እንዳልታይና እንዳይሰማብኝ ያልሠራሁትና ያልፈጸምኩት ዘድ አልነበረም። አንቺንም በጣም እፈራሽና እጠራጠርሽ ነበር» አልኩና አልጋዋ ላይ ጣል ያደረገችውን የሰነበተ ጋዜጣ ማገላበጥ ጀመርኩ። አንገቷን ወደ ቀኝ ሰበር አድርጋ የማገላብጠውን
ጋዜጣ እየተመለከተች ግን እኮ እያደር እንዳፈቀርካትና ከወዲያ ወዲህ
እየተመላለሰች በምትሠራበት ጊዜ ዐይኖችህ አብረዋት እንደሚዋትቱ ኣሳምሬ ዐውቅ ነበር፡፡ ከእንጀራ አቅም እንኳ ሌላ ሰው ሲያቀርብልህ ደስ አይልህም ነበር። እሷም የዋዛ ሾላካ አልነበረችም ! ኋላማ ልናባርራት አቅራቢያ
አረማመዷና አነጋገሯ፣ ጸጉር አሠራሯና አለባበሷ ሁሉ በጣም ተሻሽሉ ነበር፡፡
እኔ ከሁሉም ከሁሉም የማይረሳኝ ጠባይዋና ሲያዝዋት እሺ ባይነቷ ነው፡፡ ምን ይሆናል፣ ያ መሳይ መልክ ያለ ቦታው ቀረ፡፡ እሷ የተማረች ሆና ውጪ
ውጪውን ብናገኛት ኖሮ... እኔ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ስለ እሷ አንዳችም ወሬ
ሰምቼ አላውቅም» ብላ አጠናቀቀች። የወሬ ከረጢቷን መፍታቷ ስለ ታወቀኝ
ለጊዜው ውስጣዊ ብስጭቴን ኣፍኜ ባናነሣው ይሻላል ያለፈው አልፏል እንጂ
ብሳሳትም ባልሳሳትም ከዚህ ቤት ስታባርሯት እርጉዝ ነበረች። ቀስ ብላችሁ
ሹክ ብትሉኝ ኖሮ እንደምንም አንዱ ጋ አስጠጋትና ትወልድ ነበር፡፡
ይኸንዬ እኔን አባብዬ” ሲል አንቺን ደግሞ ”እቴቴ' እቴ ሸንኮሬ 'እት -አይገኝ” ይልሽ ነበር» አልኳት፡፡ የአሁኑን የ'ወዲያነሽን ሕይወትና ኑሮ የማታውቀዋ እኅቴ ከሁሉም ከሁሉም በጣም የሚያሳዝነኝ» ብላ ቀጠለች፣
«ያነዪ አንተ ወደ ሥራ ወጣ ከማለትu እማዬ በአባባ ከዘራ ታፋ ታፋዋን'
ጀርባ ጀርባዋን ስትደበድባት ኩርምት ብላ ስትደበደብ የወረደባት የዱላ መዓት ነው፡፡ በመጨረሻ የተሰነዘረው ዱላ መኻል እናቷ ላይ በማረፉ ደሟ በጸጉሯ ውስጥ እየተንጀረጀረ ትከሻዋ ላይ ተንጠፈጠፈ፡፡ ነፍስ ይዟትም ይሁን ያሰበችውን እንጃ ከዘራውን ይዛ እለቅም በማለቷ እኔም እናቴን የተዳፈረችብኝና ግብግብ የምትገጥማት ስለመሰለኝ ሁለት ጊዜ በጥፊ አላስኳት።
«እሷ ግን ቀና ብላ አይታ፣ አንቺም? አንቺም? ጨክነሽ ትመቺኝ የውብነሽ? ኣይ ድኃ መሆን!” ያለችኝ ዛሬም አንጀት አንጀቴን ይበላኛል፡፡»
«እሷ ግን በጣም የተንገበገበችውና ያለቀሰችው ከቤት በመባረሯና
በመደብደቧ ሳይሆን እንተን ሳትሰናበትሀና ሳታይህ በመሔዷ ነበር። ከሥራ ስትመለስ መንገድ ላይ ጠብቃ እንዳታግባባሀና በሴት እንባዋ እንዳታታልልህ ከዚህ አካባቢ ያባረርናት በዘበኛ ነበር» ብላ ያን ዚያ ቀደም አሳርሮ
ያከሰለኝን መራራ ነገር እንደገና ጋተችኝ፡፡ የየወዲያነሽ መከራና እንግልት
ሁሉ ከተቀበረበት የትዝብት መቃብር ወጥቶ ነጭ ዓፅሙ ፊት ለፊቴ ተገተረ፡፡ ሌላ ተጨማሪ ነገር በመስማት አንጎሌን ማጥመልመል ስላልፈለግሁ
«ነገ አራት ሰዓት ላይ ዕጓለ ማውታ ስለምሔድ አብረን እንሂድ። ከዚያ በኋላ
ደግሞ ሌላ የማማክርሽ ጉዳይ ስላለ ቀደም ብለሽ ቀበና ድልድይ አጠገብ
ጠብቂኝ ብያት ወጣሁ፡፡
በማግሥቱ እሑድ እኅቴና ባለቤቴ ዕጓለ ማውታ እንዳይገናኙብኝ፡ የወዲያነሽን «እንግዳ ይዤ እመጣለሁና ተዘጋጅተሽ እንድትጠብቂኝ፡ ከዚያ በኋላ እንሔዳለን» ብያት ከቤት ወጣሁ፡፡ መኪና መግዛቴን መላ ቤተሰቦቼ ስላልሰሙ የውብነሽ የምትጠብቀኝ በእግር እንጂ በመኪና ይመጣል ብላ አልነበረም፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ዘግየት ብዬ ቀጠሮእችን ቦታ ስደርስ የውብነሽ ተረከዘ ሹል ጫማ አድርጋ ከጉልበቷ ትንሽ ከፍ ያለ ቀለመ ብዙ የፈረንጅ ቅድ ቀሚስና ነጭ ሸሚዝ ለብሳ ቡናማ ኮረጆዋን አንግታ ድልድዩ አካባቢ ስትጠብቀኝ አገኘኋት። መኪና አጠገቧ ደርሳ በመቆሟ ባለ መኪናውም እኔ መሆኔን ባለማወቋ ፊቷን በቁጣ ከሰከሰች፡፡ እንዳንድ የጎዳና ሴቶች
ለመግደርደር ሲሉ የሚያሳዩት አኳኋን ትዝ አለኝና የየውብነሽ አድራጎት አሣቀኝ፡፡ ወዲያው ወጣ ብዬ ወደ እርሷ ተራመድኩ። ከመኪና ወጥቶ ወደ
እርሷ የሚራመደው ሰው ታላቅ ወንድሟ መሆኑን ስታውቅ የአድናቆት ሣቅ
ሣቀች፡፡
«መኪና ገዛሁ እንዳትለኝ አለችኝ፡፡ «አዎ ገዛሁ እኔም ወጉ ይድረሰኝ ብዬ ገና ሁለተኛ ወሯን መያዟ ነው» አልኩና እየተሣሣቅን ተጨባበጥን፡፡
«የውቤ፣ ይቺንም ታድያ ቤተሰብ እንዳይሰማ፣ እንድ ቀን ሁሉንም ነገር
አጠራቅሜ አቀርበዋለሁ፡፡» «ሌላ ደግሞ ምን የሚነገር አለህ?» ብላ አየችኝ፡፡
«እኔ ገና ብዙ የሚነገር ነገር አለኝ» ብያት መኪና ውስጥ ገብተን መንገድ
ቀጠልን፡፡ በአሥራ አምስት ደቂቃ ውስጥ አግድመት ቁልቁለቱን ጨርሰን
ሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅት ደረስን፡፡ ለምለሙ መስክ ላይ ትላልቅና ትናንሽ
ልጆች እንደ ጥሬ ፈስሰው ልዩ ልዩ ጨዋታዎች ይጫወታሉ። ከትንንሾቹ
ልጆች መኻል አንድ የግራ ዐይኑ የጠፋችና በዐይን አር የተጨማለቀች
ሰማያዊ ቁምጣና ትከሻው ላይ የተጣፈች እሷኑ መሰል ኮት የለበሰ ልጅ
በሩጫ መጥቶ ጨበጠኝ፡፡ የጋሻዬነህ ጓደኛ ነው:: ከኪሴ ከረሜላ ኣውጥቼ ሰጠሁት። የውብነሽ በድንጋጤ አፏን ከፍታ «ምነው ምን ሆነ? ዐይኑን ምን ነካው? ደኅና አልነበረም እንዴ !?» አለችኝ፡፡
«ይህ እኮ ያ ከዚህ ቀደም ያየሽው የጓደኛዬ ልጅ አይደለም፣ ይኸ ጓደኛዉ ነው:: አሁን ሮጦ ይጠራልናል» አልኩና የደነገጠውን ስሜቷን በደስታ
አደስኩት:: ከረሜላውን ልጦ ጎረሰና ተለይቶን ሔደ። እምብዛም ሳይቆይ
ጋሻነህን ይዞት መጣ፡፡ አንዲት በጣም የጠወለገች ነጭ አበባ ይዞ ነበረ።
እጆቼን ከብብቱ ሥር አስገብቼ በማንሣት ጉንጮቹን ስስም ሁሉም ነገር
ጥሉኝ ጠፋ፡፡ የውብነሽ ቀበል ብላ አገላብጣ ሳመችው:: ቀድሞውንም የሙት ልጅ ነው ብዬ ነግሬያት ስለ ነበር በርኅራኄ ተመለከተችው:: አላስችል ስላላት ዕንባ ተናነቃት። መሐረቧን አውጥቃ ዐይኖቿን አበሰች። «ለመሆኑ ያባቱ ዘመዶች እየመጡ ይጠይቁታል እንዴ?» አለችኝ፡፡ ልጅ ያለው መሆኑን የሰማ አንድም
👍2
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አንድ ቀን ከሰዓት በኋላ ለተለመደው የሥራ ጉዳይ ሳይሆን ለግላዊ ጉዳዩ ወደ አለቃዬ ጽሕፈት ቤት ገባሁ፡፡ በመጠኑ ግልጽ ሆኖ መናገር ፈቃድ በማግኘት በኩል ነገሩን የሚያፋጥንልኝ ስለ መሰለኝ ያጋጠመኝን ጉዳዬ ቀነጫጭቤ በሾላ በድፍን ዘዴ አስረዳሁ፡፡ ንግግሬን እንደ ጀመርኩ የወዲያነሽ ጆሮዬ ላይ ለጠፍ ብላ የምታበረታታኝ መሰለኝ፡፡
አለቃዩ አንደበቱን አለስልሶና የዝቅተኝነትን ስሜት በሚገልጹ ቃላት ተጠቅሞ የሚጠይቃቸውን ሰው ስለሚወዱ ጆሮአቸውን አቁመው ሰሙኝ::
የጉዳዩን አሳሳቢነትና መደረግ የሚገባውን ውጣ ውረድ ሁሉ ከኑሮ ልምዳቸው ስላወቁልኝ አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ እያመለከትኩ ለመሔድ እንደምችል ካንዳንድ ግዴታዎች ጋር ነገሩኝ፡፡ አዎ ጌታነህ ከባድ ግዴታ ያለብኝ ሰው ነኝ።
የመጀመሪያዋን ቃታ ሳብኩ! ማመልከቻዪን ለዕጓለ ማውታው የበላይ
ባለሥልን ለማቅረብ የሐሳቤ ዝግጅት ተጠናቀቀ። የእኔንና የባለቤቴን
የግንኙነት መነሻ፣ የወላጆቼን የአመለካከት አቋም፣ እንዲሁም የልጃችን
ሕይወት ለምንና እንዴት ለዚያ ዕጓለ ማውታ እንደበቃ ተንትኖ የሚያስረዳ
ጽሑፍ ማዘጋጀት እንዳለብኝ ከየወዲያነሽ ጋር ተነጋገርንበት።
ማታ ከት/ቤት መልስ ግራና ቀኝ ተቀምጠን ሐሳብ ለማቀነባበር
ተፍጨረጨርን፡፡ ከጉዳዩ አፈጻጸም ጋር በጣም ተፃራሪ የሆነ አቋም ቢኖረኝም ሁኔታውን ሁሉ ተቋቁሞ ሌላ አመቺ ሁኔታን መፍጠር ግን የማይቀር ግዴታ ሆነ፡፡ በመጠኑ ሞጫጭሬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ገደማ ለወጉ ያህል ጋደም አልኩ።ቁንጫውን ለማራገፍ እንደሚንደባለል ውሻ አልጋዩ ላይ መንከባለል እንጂ እንቅልፍ በማጣቴ ሁለት ሰዓት ያህል ቆይቼ ተነሣሁ፡፡ አካባቢዬ ጸጥ በማለቱ ሐሳቤን በቅደም ተከተል ለማስፈር ውጫዊ ችግር አልገጠመኝም፡፡ ምንም እንኳ የእኔና የወዲያነሽ የሕይወት ገድል በሁለትና በሦስት ገጽ ጽሑፍ ተዘርዝሮ የማያልቅ ቢሆንም መቆነጻጸሉ ግን የግድ አስፈላጊ ነበር፡፡ የወዲያነሽ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ሠራተኛ ሆና ማገልገሏን፣ በእርግዝናዋ
ወራት ከቤት መባረሯን፣ የእኔን ማንነትና ያረገዘችውም ከእኔ እንደ ነበር፣
በችግርና በእጦት ተንገላታ ልጅዋን በጭካኔ ሳይሆን በአስገዳጅ የኑሮና የጊዜ ሁኔታ አሳዳጊ እንዲያገኝ ብላ ጥላው መጥፋቷን፣ ከዚያም በወንጀለኛነት ተይዛ አምስት ዓመት መታሰሯን፡ ልጁም በድርጅቱ አማካይነት በማደግ ላይ መሆኑን በልክ በልኩ አሳምሬ ጻፍኩ፡፡ በተጨማሪም እኔና የልጄ እናት በነበረንና ባለን እውነተኛ ፍቅር ትዳር መሥርተን ኣብረን በመኖር ላይ
መሆናችንን አከልኩበት። ቀላል በሆነ አገላለፅ የተቀነባበረ ማመልከቻ
ተዘጋጀ፡፡
በመጨረሻም ድርጅቱ ይህን እስከ ዛሬ ድረስ በጥንቃቄ ያሳደገልንን ልጅ በሕጋዊ መንገድ አስረክቦን ልጃችንን ማሳደግ እንችል ዘንድ የሚጠይቅ ማለፊያ መደምደሚያ አደረግሁለት። ረቂቁን ገልብጬ ስጨርስ ሰማይና መሬት ተላቀቀ። የወዲያነሽ ከእንቅልፏ ነቃች፡፡ አልጋውና የተቀመጥኩበት ወንበር አፍና አፍንጫ ነበሩ። መለስ ብዬ ስመለከታት ካንገቷ ቀና ብላ በድንጋጤ ታስተውለኛለች፡፡ እጆቿን በትከሻዬ ላይ አሳልፋ ጣቶቿን ደረቴ ላይ አንጠለጠለቻቸው። የተበታተነው ጸጉሯ አንገቴ ላይ ሲኩነሰነስ በጣም
እንደ ተጠጋችኝ አወቅሁ፡፡ ተቀምጬ በማደሬ አካላቴ ዝሏል፡፡ የወዲያነሽን
ሐሳብ ላይ ጣልኳት፡፡ በቀኙ ትከሻዬ ላይ ደፋ አለች። በአንገቴ ሥር የተጋደመውን ክንዷን እየደባበስኩ «እንግዲህ አንድ ጊዜ ጀምሬዋለሁ፣ ፍጻሜውን ሳላይ ፊቴን አላዞርም» አልኩና ጽሑፉን አነበብኩላት። የሐሳብ ሰመመን ይዟት ነጎደ። የጻፍኩትን ማመልከቻ ሳጣጥፍ በአእምሮዬ ውስጥ
የተረገዘው ፍላጎቴ ዕለተ ልደቱ እንደ ደረሰ ታወቀኝ፡፡ ውጤቱን በግምት ሳሰላስል የወዲያነሽ ከአልጋው ላይ ወረደች፡፡
ቁርሴን በልቼ ከቤት ስወጣና መኪና አስነሥቼ ስሔድ የማልመለስ ስለ መሰላት ዐይኖቿ ከላዪ ላይ ሳይነቀሉ ተለይቻት ሔድኩ።
ማመልከቻዬን ለባለ ሥልጣኑ ከማቅረቤ በፊት መኪናዬ ውስጥ ሁለት ጊዜ ወጣሁት። የድፍረት ወኔ አጥለቀለቀኝ፡፡ አረማመዴ ጎምላላ ሆነ።አንኳኩቼ ስገባ መላ ሰውነቴ ተሟሟቀ። ማመልከቻዬን ሳቀርብ በሐተታው ርዝመት እንጂ በዘረዘርኩት ከፊል ምስጢር ቅንጣት ታህል አላፈርኩም፡፡አያሳፍርማ!! እንዲያውም ማቀርቀሬና መደንገጤ ቀርቶ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማቅረብ ተዘጋጀሁ፡፡ ለሦስት ደቂቃዎች ያህል ታሪኩን ያላንዳች እንቅስቃሴ
አነበቡት። የታሪኩ አነሳና አካሔድ ስላስደነቃቸው ራሳቸውን ይነቀንቁ
ጀመር፡፡ ስሜታቸውና ሁኔታቸው ስላፍነከነከኝ የተስፋ ምጥ አጣደፈኝ፡፡
የሚያስደንቅ ዐረፍተ ነገር ሲያጋጥማቸው ንባባቸውን እያቋረጡ ስለሚመለከቱኝ የምትወጂውን ታሚያለሽ እንደ ተባለች ፈሰሰ ሁለመናዬ በደስታ ተነከረ፡፡ ሁለቱን ገጾች ጨርሰው ሦስተኛዉን ሲጀምሩ ወረቀቱን አጠፍ አድርገው ጠረጴዛውን በሁለት ክንዳቸው ተመረኮዙ። ከእግር ጥፍሬ እስከ ራስ ጸጉሬ ተመለከቱኝ። እንደገና ደግሞ «ልጄን በችግርና በሥቃይ ከመግደል ይልቅ ምናልባት ርኅሩኅ አሳዳጊና ሰብሳቢ ቢያገኝ ብዩ ብዙ ሕዝብ ከሚተላለፍበት መንገድ
ላይ በጨርቅ ጠቅልዩ ጣልኩት» የሚለውን የእናትየዋን አነጋገር ጽፌው ስለ ነበር ጮክ ብለው አነበቡት።
ምንም እንኳን እሷን ለመርዳትና ልጀንም ለማሳደግ ሙሉ ችሎታ ቢኖረኝም ከቤት የተባረረችው በሌለሁበት ጊዜ ስለነበርና ኋላም አድራሻዋን ለማግኘት ባለመቻሌ ይህ የአንድ ትውልድ የመጥፎ ልማድ ድርሻ ሊደርስብን ቻሏል የሚለውን ሐተታ በቀዳሚው የድምፅ ሁኔታ ደገሙት። አንብበው ከጨረሱ በኋላ ላቀረቡልኝ ጥያቄ የተብራራ ኣጥጋቢ መልስ ሰጠሁ፡፡ ጥያቄ በሚያቀርቡበትና መልስ በሚሰሙበት በሚያደርጉት ከፍተኛ ጥንቃቄ የጦር ስልት እንዳይበላሽበት የሚከታተልና የውጊያ ስልት ሚዛን የሚቆጣጠር የጦር አበጋዝ ይመስላሉ፡፡ መልሶቼን ሁሉ እያጣጣሙ ተራ በተራ ዋጧቸው::
ለእርሳቸው የአንድ ጉዳይ ተራ ውጥን ቢሆንም፡ ለእኔ ግን አንድ አነስተኛ የትግል ምዕራፍ ነበር፡፡ ሙሉ ተስፋ በማይሰጥ ሁኔታ ቀጠሮ ተቀብዩ ወጣሁ፡፡
ጉዳዩ በቀላሉ የማይፈጸም በመሆኑ ድርጅቱ ጥያቄውን አብላልቶ ከአንድ ውሳኔ ላይ ለመድረስ በጉዳዩ ላይ አተኮረበት።
ደጅ ደጁን ፍሬ ሐሳብ የሚያቀብለኝና በጎደለ የሚሞላልኝ ጉልላት ነበር፡፡ በየቀጠሮው ቀን ስቀርብ የሚጠብቀኝ ጥያቄ ከዕለት ወደ ዕለት እንደ
ስንቅ ሟሸሸ፡፡
አነጣጥሬ የለቀቅሁት የሰላም ቀስት ዒላማውን መታ፡፡ ልክ ባሽመቅሁ
በኻያ አንደኛዉ ቀን የድርጅቱ ደንብ እና ሌላውም ሕግ በሚፈቅደው መሠረት ልጁን የምረከብበት ቀን ተነገረኝ፡፡ ባለቤትህን ይዘህ እንድትቀርብ
ተብዬ ስለ ነበር የወዲያነሽን ተነሽ አልኳት፡፡ ዶፍ እንደ ወረደበት የፍየል
ግልገል አካላቷ ተሽማቀቀ፡፡ ልማደኛ እንባዋ አትንካት ሲል ተንቆረዘዘ፡፡
አስታራቂ ሐሳብ ስላልነበረ ተረታች፡፡ «እንዴት ብዩ ከሰው ፊት እቀርባለሁ?
ያለፈውን አድራጎቴን ሁሉ ቢጠይቀኝስ ምን እመልሳለሁ? ይቺ ጨካኝ
አረመኔ ቢሉኝስ ምን እላለሁ? አንተን እንዳልኩህ ነው የምላችው?» ብላ
በሥጋት ጠየቀችኝ። እእምሮዋ ተናውጦ እንዳይናጋ የፈጸምሽው ሁሉ በወቅቱ
ባጋጠመሽ አስገዳጅ ሁኔታ የተደረገ ተራ ድርጊት እንጂ ይህን ሁሉ አጓጉል
ስያሜ የሚያሰጥ ባለመሆኑ አታስቢ» ብዩ ካግባባኋት በኋላ ሄድን።
በመንገድ ላይና ድርጅቱም ጽሕፈት ቤት ከመግባታችን በፊት በጣም ስለ አበረታታኋት አራት የድርጅቱ ባለሥልጣኖች በተሰበሰቡበት ክፍል ውስጥ ለጥያቄዎቻቸው ሁሉ መልስ እንድትሰጥና ሐሳቧንም ያላንዳች ግፊት
እንዲሰሙ ጥያት ወጣሁ፡፡ በአስተዋይነቷ ስለምተማመን ምን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አንድ ቀን ከሰዓት በኋላ ለተለመደው የሥራ ጉዳይ ሳይሆን ለግላዊ ጉዳዩ ወደ አለቃዬ ጽሕፈት ቤት ገባሁ፡፡ በመጠኑ ግልጽ ሆኖ መናገር ፈቃድ በማግኘት በኩል ነገሩን የሚያፋጥንልኝ ስለ መሰለኝ ያጋጠመኝን ጉዳዬ ቀነጫጭቤ በሾላ በድፍን ዘዴ አስረዳሁ፡፡ ንግግሬን እንደ ጀመርኩ የወዲያነሽ ጆሮዬ ላይ ለጠፍ ብላ የምታበረታታኝ መሰለኝ፡፡
አለቃዩ አንደበቱን አለስልሶና የዝቅተኝነትን ስሜት በሚገልጹ ቃላት ተጠቅሞ የሚጠይቃቸውን ሰው ስለሚወዱ ጆሮአቸውን አቁመው ሰሙኝ::
የጉዳዩን አሳሳቢነትና መደረግ የሚገባውን ውጣ ውረድ ሁሉ ከኑሮ ልምዳቸው ስላወቁልኝ አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ እያመለከትኩ ለመሔድ እንደምችል ካንዳንድ ግዴታዎች ጋር ነገሩኝ፡፡ አዎ ጌታነህ ከባድ ግዴታ ያለብኝ ሰው ነኝ።
የመጀመሪያዋን ቃታ ሳብኩ! ማመልከቻዪን ለዕጓለ ማውታው የበላይ
ባለሥልን ለማቅረብ የሐሳቤ ዝግጅት ተጠናቀቀ። የእኔንና የባለቤቴን
የግንኙነት መነሻ፣ የወላጆቼን የአመለካከት አቋም፣ እንዲሁም የልጃችን
ሕይወት ለምንና እንዴት ለዚያ ዕጓለ ማውታ እንደበቃ ተንትኖ የሚያስረዳ
ጽሑፍ ማዘጋጀት እንዳለብኝ ከየወዲያነሽ ጋር ተነጋገርንበት።
ማታ ከት/ቤት መልስ ግራና ቀኝ ተቀምጠን ሐሳብ ለማቀነባበር
ተፍጨረጨርን፡፡ ከጉዳዩ አፈጻጸም ጋር በጣም ተፃራሪ የሆነ አቋም ቢኖረኝም ሁኔታውን ሁሉ ተቋቁሞ ሌላ አመቺ ሁኔታን መፍጠር ግን የማይቀር ግዴታ ሆነ፡፡ በመጠኑ ሞጫጭሬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ገደማ ለወጉ ያህል ጋደም አልኩ።ቁንጫውን ለማራገፍ እንደሚንደባለል ውሻ አልጋዩ ላይ መንከባለል እንጂ እንቅልፍ በማጣቴ ሁለት ሰዓት ያህል ቆይቼ ተነሣሁ፡፡ አካባቢዬ ጸጥ በማለቱ ሐሳቤን በቅደም ተከተል ለማስፈር ውጫዊ ችግር አልገጠመኝም፡፡ ምንም እንኳ የእኔና የወዲያነሽ የሕይወት ገድል በሁለትና በሦስት ገጽ ጽሑፍ ተዘርዝሮ የማያልቅ ቢሆንም መቆነጻጸሉ ግን የግድ አስፈላጊ ነበር፡፡ የወዲያነሽ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ሠራተኛ ሆና ማገልገሏን፣ በእርግዝናዋ
ወራት ከቤት መባረሯን፣ የእኔን ማንነትና ያረገዘችውም ከእኔ እንደ ነበር፣
በችግርና በእጦት ተንገላታ ልጅዋን በጭካኔ ሳይሆን በአስገዳጅ የኑሮና የጊዜ ሁኔታ አሳዳጊ እንዲያገኝ ብላ ጥላው መጥፋቷን፣ ከዚያም በወንጀለኛነት ተይዛ አምስት ዓመት መታሰሯን፡ ልጁም በድርጅቱ አማካይነት በማደግ ላይ መሆኑን በልክ በልኩ አሳምሬ ጻፍኩ፡፡ በተጨማሪም እኔና የልጄ እናት በነበረንና ባለን እውነተኛ ፍቅር ትዳር መሥርተን ኣብረን በመኖር ላይ
መሆናችንን አከልኩበት። ቀላል በሆነ አገላለፅ የተቀነባበረ ማመልከቻ
ተዘጋጀ፡፡
በመጨረሻም ድርጅቱ ይህን እስከ ዛሬ ድረስ በጥንቃቄ ያሳደገልንን ልጅ በሕጋዊ መንገድ አስረክቦን ልጃችንን ማሳደግ እንችል ዘንድ የሚጠይቅ ማለፊያ መደምደሚያ አደረግሁለት። ረቂቁን ገልብጬ ስጨርስ ሰማይና መሬት ተላቀቀ። የወዲያነሽ ከእንቅልፏ ነቃች፡፡ አልጋውና የተቀመጥኩበት ወንበር አፍና አፍንጫ ነበሩ። መለስ ብዬ ስመለከታት ካንገቷ ቀና ብላ በድንጋጤ ታስተውለኛለች፡፡ እጆቿን በትከሻዬ ላይ አሳልፋ ጣቶቿን ደረቴ ላይ አንጠለጠለቻቸው። የተበታተነው ጸጉሯ አንገቴ ላይ ሲኩነሰነስ በጣም
እንደ ተጠጋችኝ አወቅሁ፡፡ ተቀምጬ በማደሬ አካላቴ ዝሏል፡፡ የወዲያነሽን
ሐሳብ ላይ ጣልኳት፡፡ በቀኙ ትከሻዬ ላይ ደፋ አለች። በአንገቴ ሥር የተጋደመውን ክንዷን እየደባበስኩ «እንግዲህ አንድ ጊዜ ጀምሬዋለሁ፣ ፍጻሜውን ሳላይ ፊቴን አላዞርም» አልኩና ጽሑፉን አነበብኩላት። የሐሳብ ሰመመን ይዟት ነጎደ። የጻፍኩትን ማመልከቻ ሳጣጥፍ በአእምሮዬ ውስጥ
የተረገዘው ፍላጎቴ ዕለተ ልደቱ እንደ ደረሰ ታወቀኝ፡፡ ውጤቱን በግምት ሳሰላስል የወዲያነሽ ከአልጋው ላይ ወረደች፡፡
ቁርሴን በልቼ ከቤት ስወጣና መኪና አስነሥቼ ስሔድ የማልመለስ ስለ መሰላት ዐይኖቿ ከላዪ ላይ ሳይነቀሉ ተለይቻት ሔድኩ።
ማመልከቻዬን ለባለ ሥልጣኑ ከማቅረቤ በፊት መኪናዬ ውስጥ ሁለት ጊዜ ወጣሁት። የድፍረት ወኔ አጥለቀለቀኝ፡፡ አረማመዴ ጎምላላ ሆነ።አንኳኩቼ ስገባ መላ ሰውነቴ ተሟሟቀ። ማመልከቻዬን ሳቀርብ በሐተታው ርዝመት እንጂ በዘረዘርኩት ከፊል ምስጢር ቅንጣት ታህል አላፈርኩም፡፡አያሳፍርማ!! እንዲያውም ማቀርቀሬና መደንገጤ ቀርቶ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማቅረብ ተዘጋጀሁ፡፡ ለሦስት ደቂቃዎች ያህል ታሪኩን ያላንዳች እንቅስቃሴ
አነበቡት። የታሪኩ አነሳና አካሔድ ስላስደነቃቸው ራሳቸውን ይነቀንቁ
ጀመር፡፡ ስሜታቸውና ሁኔታቸው ስላፍነከነከኝ የተስፋ ምጥ አጣደፈኝ፡፡
የሚያስደንቅ ዐረፍተ ነገር ሲያጋጥማቸው ንባባቸውን እያቋረጡ ስለሚመለከቱኝ የምትወጂውን ታሚያለሽ እንደ ተባለች ፈሰሰ ሁለመናዬ በደስታ ተነከረ፡፡ ሁለቱን ገጾች ጨርሰው ሦስተኛዉን ሲጀምሩ ወረቀቱን አጠፍ አድርገው ጠረጴዛውን በሁለት ክንዳቸው ተመረኮዙ። ከእግር ጥፍሬ እስከ ራስ ጸጉሬ ተመለከቱኝ። እንደገና ደግሞ «ልጄን በችግርና በሥቃይ ከመግደል ይልቅ ምናልባት ርኅሩኅ አሳዳጊና ሰብሳቢ ቢያገኝ ብዩ ብዙ ሕዝብ ከሚተላለፍበት መንገድ
ላይ በጨርቅ ጠቅልዩ ጣልኩት» የሚለውን የእናትየዋን አነጋገር ጽፌው ስለ ነበር ጮክ ብለው አነበቡት።
ምንም እንኳን እሷን ለመርዳትና ልጀንም ለማሳደግ ሙሉ ችሎታ ቢኖረኝም ከቤት የተባረረችው በሌለሁበት ጊዜ ስለነበርና ኋላም አድራሻዋን ለማግኘት ባለመቻሌ ይህ የአንድ ትውልድ የመጥፎ ልማድ ድርሻ ሊደርስብን ቻሏል የሚለውን ሐተታ በቀዳሚው የድምፅ ሁኔታ ደገሙት። አንብበው ከጨረሱ በኋላ ላቀረቡልኝ ጥያቄ የተብራራ ኣጥጋቢ መልስ ሰጠሁ፡፡ ጥያቄ በሚያቀርቡበትና መልስ በሚሰሙበት በሚያደርጉት ከፍተኛ ጥንቃቄ የጦር ስልት እንዳይበላሽበት የሚከታተልና የውጊያ ስልት ሚዛን የሚቆጣጠር የጦር አበጋዝ ይመስላሉ፡፡ መልሶቼን ሁሉ እያጣጣሙ ተራ በተራ ዋጧቸው::
ለእርሳቸው የአንድ ጉዳይ ተራ ውጥን ቢሆንም፡ ለእኔ ግን አንድ አነስተኛ የትግል ምዕራፍ ነበር፡፡ ሙሉ ተስፋ በማይሰጥ ሁኔታ ቀጠሮ ተቀብዩ ወጣሁ፡፡
ጉዳዩ በቀላሉ የማይፈጸም በመሆኑ ድርጅቱ ጥያቄውን አብላልቶ ከአንድ ውሳኔ ላይ ለመድረስ በጉዳዩ ላይ አተኮረበት።
ደጅ ደጁን ፍሬ ሐሳብ የሚያቀብለኝና በጎደለ የሚሞላልኝ ጉልላት ነበር፡፡ በየቀጠሮው ቀን ስቀርብ የሚጠብቀኝ ጥያቄ ከዕለት ወደ ዕለት እንደ
ስንቅ ሟሸሸ፡፡
አነጣጥሬ የለቀቅሁት የሰላም ቀስት ዒላማውን መታ፡፡ ልክ ባሽመቅሁ
በኻያ አንደኛዉ ቀን የድርጅቱ ደንብ እና ሌላውም ሕግ በሚፈቅደው መሠረት ልጁን የምረከብበት ቀን ተነገረኝ፡፡ ባለቤትህን ይዘህ እንድትቀርብ
ተብዬ ስለ ነበር የወዲያነሽን ተነሽ አልኳት፡፡ ዶፍ እንደ ወረደበት የፍየል
ግልገል አካላቷ ተሽማቀቀ፡፡ ልማደኛ እንባዋ አትንካት ሲል ተንቆረዘዘ፡፡
አስታራቂ ሐሳብ ስላልነበረ ተረታች፡፡ «እንዴት ብዩ ከሰው ፊት እቀርባለሁ?
ያለፈውን አድራጎቴን ሁሉ ቢጠይቀኝስ ምን እመልሳለሁ? ይቺ ጨካኝ
አረመኔ ቢሉኝስ ምን እላለሁ? አንተን እንዳልኩህ ነው የምላችው?» ብላ
በሥጋት ጠየቀችኝ። እእምሮዋ ተናውጦ እንዳይናጋ የፈጸምሽው ሁሉ በወቅቱ
ባጋጠመሽ አስገዳጅ ሁኔታ የተደረገ ተራ ድርጊት እንጂ ይህን ሁሉ አጓጉል
ስያሜ የሚያሰጥ ባለመሆኑ አታስቢ» ብዩ ካግባባኋት በኋላ ሄድን።
በመንገድ ላይና ድርጅቱም ጽሕፈት ቤት ከመግባታችን በፊት በጣም ስለ አበረታታኋት አራት የድርጅቱ ባለሥልጣኖች በተሰበሰቡበት ክፍል ውስጥ ለጥያቄዎቻቸው ሁሉ መልስ እንድትሰጥና ሐሳቧንም ያላንዳች ግፊት
እንዲሰሙ ጥያት ወጣሁ፡፡ በአስተዋይነቷ ስለምተማመን ምን
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጉልላት ሙሽራ ይዞ እንደሚመለስ ሚዜ በደስታ ብዛት ከወዲያ ወዲህ ይዞራል፡፡ እኔ ግን እምብዛም አያሌ ለውጥ የሚገኝበት ሕይወትና የኑሮ አካባቢ እንደማይጠብቀው ስለማውቅ አልፈነደቅሁም፡፡ በአካባቢው የነበሩት
ሰዎች ሁሉ እኔንና የወዲያነሽን «እንኳን ደስ ያላችሁ! እሱንም እንኳን ለዚህ
እበቃው!? እያሉ መልካም ምኞታቸውን ገለጹልን፡፡ የወዲያንሽ ከፍተኛ ደስታ
ስላጥለቀለቃት የሚፈጸመውንና የሚነገረውን ሁሉ የምትከታተልና
የምታዳምጥ ኣትመስልም፡፡ የድርጅቱ ተወካይ ባለሥልጣን ጋሻዬነህን ጎንበስ
ብለው ካነሡ በኋላ በወዳጅነት ፈገግታ ተዝናንተው «ለቁም ነገር የሚበቃና
የተባረከ፣ እናት አባቱን አክባሪ ጧሪ ቀባሪና አስመስጋኝ ልጅ እንዲሆንላችሁ
እመኛለሁ» ብለው ጋሻዬነህን ለየወዲያነሽ አስረከቧት፡፡ የጋሻዬነህ እጅ
በየወዲያነሽ አንገት ዙሪያ ተጠመጠመች ጉልላት ከአበባ ወደ አበባ ለቀሠማ
እንደምትዘዋወር ንብ ሰውን ሁሉ ይዞረዋል። የወዲያነሽ ሰውነቷ እየተንዘፈዘፈ የደስታ እንባ አነባች፡፡ የንጋት ፀሐይ ጨረር እንዳረፈበት የባቄላ አበባ
የሚያስደስተው ጥርሷ ፍልቅቅ ብሎ በመታየት የውስጣዊ ደስታዋ ምስክር
ነበር፡፡ ደስታና ትዝታ ተቃረጧት፡፡ «ቀስ በቀስ ደስታዬ ውስጥ ውስጡን
እንደ እሳተ ገሞራ ፍል እየተንሸከሽከ ሰውነቴን አሞቀው፡፡ የወዲያነሽ
ጉጉትና ምኞት ተፈጸመ፡፡ ወዴት እንደሚወሰድ የማያውቀው ጋሻዬነህም
ከእናቱ ትከሻ ባሻገር ወደ ኋላ እየተመለከተ የስድስት ዓመታት መኖሪያውን ለቅቆ ወጣ፡፡
ጋሻዬነህን ይዘን ወደ ቤት ስንገባ ቀደም ብለው ወሬውን የሰሙት ሦስት ወራት ያህል የቅርብ ጎረቤቶቻችን በሙሉ ደስታ ተቀበሉን፡፡ የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አቅፋ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች። ጋሻዬነህ ግራ ገባው። በማያውቀው አዲስ አካባቢ በመገኘቱ ተጨነቀ፡፡ ዐይኖቹ ተቅበዘበዙ፡፡ የቤቱ ዕቃና በዙሪያው ያሉት ሰዎች ሁሉ አዲስ ስለ ሆኑበት ቀስ እያለ በፍርሃት ዐይን አያቸው። የለበሰው ነጭ ልብስና የእናቲቱ አረንጓዴ ቀሚስ በአንድነት ሲታዩ በቄጠማ መኻል የበቀለች ነጭ አበባ መሰሉ፡፡ የተደረገው ውጣ ውረድ ሁሉ
አስደሰተኝ፡፡
እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ለሚመጡት የጎረቤት ሰዎች ከወዲያ ወዲህ እያሉ ጠላ የሚቀዱት ጉልላትና ሠራተኛችን ነበሩ፡፡ የወዲያነሽማ ከተቀመጠችበት የምትነሣ አትመስልም ነበር፡፡ የሰው ሁሉ ዐይን በእናትና ልጅ ላይ አረፈ። «እንኳን ለዚህ አበቃሽ! እንኳን ደስ ያላችሁ፣ እሰየው እሰይ» እያሉ የሚስሙን የሰፈሩ ሰዎች ደስታችን ደስታቸው ሆነ። ጋሻዬነህ
መላ ቅጡ ጠፋው። ከእናቱ ተቀብዬ ስታቀፈው ከጭልፊት አምልጣ ከጭራሮ
መዝጊያ ሥር እንደምትሸጎጥ ጫጩት ደረቴ ላይ ተለጠፈ፡፡ ዐሥር ሰዓት
ገደማ ጉልላት፣ እኔና የወዲያነሽ እንዲሁም የቤታችን አዲሱ 'ሰው' ብቻ
ቀረን፡፡ የቤቱን ወለል ለመንካት የፈራ ይመስል ከእኔና ከእናቱ ዕቅፍ
አልላቀቅ አለ። ካፈናት የደስታ ሲቃ ጋር ትንሽ በትንሽ ስለ ተለማመደችና
የጎጆ ነገር በመሆኑ የወዲያነሽ ጉድ ጉድ አለች፡፡ ጋሻዬነህንም በእጅዋ ይዛ
ከመኝታ ቤት ወደ ትልቁ ክፍል ከዚያም ወደ ውጭና ወደ ግቢው እየወሰደች
አዝናናችው፡፡ በፍርሃት ተሳስሮ የቆየው ሰውነቱ በመፍታታቱ በፊቱ ላይ
የፈገግታ ጮራ ታየ፡፡ የቤቱን ውስጥ ዕቃዎች አንድ በአንድ እያየ መደባበስ
ጀመረ፡፡
ከዚያም ዐልፎ ”እማማ” እያለ ጥያቄ ማቅረብ ቀጠለ፡፡ ከሁሉም ከሁሉም እማሚ የምትለዋ ቃሉ ልቤን በደስታ ዘርፍ አሳመረቻት፡፡ የጉልላትን ዐመል የምታውቀዋ የወዲያነሽ ወፍራም ሻይ አቀረበችለት፡፡ የሚፈልገውን ያህል ስላላነቃቃው ጋደም አለ፡፡ የጋሻዬነህ አእምሮ ከአካባቢው ጋር ተላምዶ ፍርሃቱ በመቃለሉ ብቻውን በሰበሰቡ ላይ መሯሯጥና ዕንጨቱን እያሻሽ መጫወት ጀመረ፡፡ ትዎትም ትም እያደረገ በፍጥነት በሚራመድበት ጊዜ አንገቴን እርሱ ወዳለበት ቦታ አስግና «ቀስ! ቀስ እያልክ እንዳትወድቅ፣ ረጋ ብለህ ነው መጫወት! እያልኩ ማስጠንቀቂያ ለመስጠት በመብቃቴ ያባትነት ኩራት ተሰማኝ፡፡ ድንገት እግሩ ከእግሩ ጋር ተጋጭቶ ወይም አንሸራቶት ሲወድቅ «አይዞህ! የኔ አንበሳ! » ብዬ ላነሳው በመሮጤ አንጎሌ
በደስታ ሰከረ፡፡ የዕለቷ ፀሐይ ግዴታዋን ጨርሳ ስትሰናበት ጉልላትንጰለመሸኘት ወጣሁ፡፡
የዚያች የጋግርታም መኪናው ሞተር ፍዳችንን አሳየን። «ሙክት ሲያጡ ወጠጤ አርደው ድግስን ይወጡ» ሆነና የእኔዋን ይዞ ሔደ፡፡ ቀኑም ሆነ ምሽቱ እንደዚያ ዕለት አጥሮብኝና ፈጥኖብኝ አያውቅም፡፡ ጊዜ የሚጨበጥ ግዙፍ ኣካል ቢሆን ኖሮ ይለይልን ነበር፡፡
አዲስ መዐድ ! በቀዳሚ ትግልና ድል ያጌጠ መዐድ! ከነጠላ ወደ ስሉስ አካላት የተሸጋገረ መዐድ! ያቺ የሁለት ቀን የወንደላጤነት ቤቴ ቀደም ሲል በየወዲያነሽ ዛሬ ደግሞ ጋሻዬነህ ደምቃ ምሰሶዋ ወፈረ።ለመጀመሪያ ጊዜ በመዐዳችን ዙሪያ ሦስት ማእዘን ሆነን ተቀመጥን። የተስፋዬ ዘለላ ተጨባጭ ፍሬ አፈራ፡፡ የመከራ ቀንበሯ ገና ያልተሰበረው የወዲያነሽ፡አረሠብሩህ ተስፋ ያለውና የሥቃይ ፍሬ የሆነው ጋሻዬነህ፣ ያን ሁሉ የኑሮ ኮረኮንች አልፈውና፡ ከፊት ለፊት ያለውን ጉራንጉራም የሕይወት ወጣ ገባ
እና የኑሮ ጭጋግ ከእኔ ጋር አብሮ ለመጋፈጥ ተገናኘን፡፡
ሕሊናችን በደስታ በመሞላቱ ሆዳችን ጠገበ፡፡ ችግር የተፈጠረው መኝታ ላይ ነበር፡፡ እኔ በበኩሌ ወደ እኔ ዞሮ አቅፌውና አቅፎኝ እንዲተኛ ስፈልግ፣ እናቱ ደግሞ «ኧረ ምን ሲደረግ አንተ እኮ አምስት ዓመት ሙሉ እስኪበቃህ አይተህ ጠግበኸዋል» ብላ አሻፈረኝ አለች፡፡ ወዲያ ብል ወዲህ ብል ተሸነፍኩ፡፡ ካንገት በላይ እሷን ያናደድኩ መስሎኝ ወደ ግድግዳው ዞሬ ተኛሁ፡፡ ዝም ብላ በመተኛት ፈንታ ቀስ እያለች ከልጅዋ ጋር ወሬዋን ቀጠለች፡፡ ትኩስ የአባትነት ቅናት አላስተኛ ስላለኝ ያለ ምክንያት መገላበጥና ማካክ አበዛሁ፡፡ የልጅዋን እጅ ባንገቷ ዙሪያ ጠምጥማ የናፍቆት ጥማቷን የምታረካዋ የወዲያነሽ «እባክህ አርፈህ ተኛ! አሁን ምን ሆንኩ ብለህ ነው
የምትገላበጠው?» አለችኝ፡፡ «አማረብኝ ብለሽ ነው? ጠቦሽ እንደሆነ ልነሣና
ልውረድ፣ አበዛሽው! » አልኩና ፍቅራዋ ቅናቴ ስለ ገነፈለብኝ «አምጪ!
አይቻልም፣ መተኛት ያለበት በእኔና በአንቺ መካከል ነው! » ብዩ አስገዳጅ
ቃላት ተናገርኩ፡፡ ከት ብላ ስቃ ጋሻዬነህን በላይዋ ላይ አሳልፋ በመካከላችን
አስተኛችው፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የሁለታችንን ክንዶች ተንተርሶ ሲተኛ ለውጡ ምን ስሜት እንደ ፈጠረበት ለማወቅ ጓጓሁ፡፡ ሙያዩ ባለመሆኑ አቃተኝ፡፡ የብልጠቴ ብልጠት ባፍንጫው በኩል የምትወጣዋን ትንፋሹን ለማዳመጥ ስል ራሱን ወደ እኔ ኣስጠጋሁት:: ጧት ግን በዕለቱ ሥራ ምክንያት ማልዳ በመነሣቷ ከጋሻዬነህ ጋር ሰፊ ልፊያና ጨዋታ ቀጠልኩ። አንዳንድ ጊዜ ወደ እኛ ዘንድ ትመጣና «በል ይውልህ! በዚህ አያያዝማ ምኑን ተነሣኸው?» ትልና ወደ ሥራዋ ትመለሳለች:: ቆየትየት ብላ ደግሞ ትመስስና «እኔ ምኑም ምኑም አልተሠራልኝም እንዳፈቀዳት አድርጋ ትሥራው:: የእናንተ ጨዋታ ናፈቀኝ» በማለት አልጋው ጫፍ ላይ እረፍ ብላ እሽቆልቁላ ትመለከተን ነበር፡፡
ያም ሆነ ይህ የጋራ ቀንዲላችን ፏ ብሉ በራ፡፡ የእኔና የወዲያነሽ የአንድነት እና የጋራ ችቦ ተንቦለቦለ፡፡ ነበልባሉ እንዳይጠፋኛ ፍሙ እንዳይከስም ፍቅራችን የነዳጅ ኃይል ሰጠው:: የሳምንቱ ቀናት እንደ ነባር አመጣጣቸው ተራ በተራ ለዘለዓለም ባለፉ ቁጥር የጋሻዬነህ ሕይወት ለውጥ ማግኘቷን ቀጠለች፡፡ «እማማዩና አባባዬ» የሚሉት ቃላት ቀስ በቀስ ተዋሐዱት፡፡ ጠባዩን ለማስተካከልና ለማረቅ እዚህ ግባ የሚባል
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጉልላት ሙሽራ ይዞ እንደሚመለስ ሚዜ በደስታ ብዛት ከወዲያ ወዲህ ይዞራል፡፡ እኔ ግን እምብዛም አያሌ ለውጥ የሚገኝበት ሕይወትና የኑሮ አካባቢ እንደማይጠብቀው ስለማውቅ አልፈነደቅሁም፡፡ በአካባቢው የነበሩት
ሰዎች ሁሉ እኔንና የወዲያነሽን «እንኳን ደስ ያላችሁ! እሱንም እንኳን ለዚህ
እበቃው!? እያሉ መልካም ምኞታቸውን ገለጹልን፡፡ የወዲያንሽ ከፍተኛ ደስታ
ስላጥለቀለቃት የሚፈጸመውንና የሚነገረውን ሁሉ የምትከታተልና
የምታዳምጥ ኣትመስልም፡፡ የድርጅቱ ተወካይ ባለሥልጣን ጋሻዬነህን ጎንበስ
ብለው ካነሡ በኋላ በወዳጅነት ፈገግታ ተዝናንተው «ለቁም ነገር የሚበቃና
የተባረከ፣ እናት አባቱን አክባሪ ጧሪ ቀባሪና አስመስጋኝ ልጅ እንዲሆንላችሁ
እመኛለሁ» ብለው ጋሻዬነህን ለየወዲያነሽ አስረከቧት፡፡ የጋሻዬነህ እጅ
በየወዲያነሽ አንገት ዙሪያ ተጠመጠመች ጉልላት ከአበባ ወደ አበባ ለቀሠማ
እንደምትዘዋወር ንብ ሰውን ሁሉ ይዞረዋል። የወዲያነሽ ሰውነቷ እየተንዘፈዘፈ የደስታ እንባ አነባች፡፡ የንጋት ፀሐይ ጨረር እንዳረፈበት የባቄላ አበባ
የሚያስደስተው ጥርሷ ፍልቅቅ ብሎ በመታየት የውስጣዊ ደስታዋ ምስክር
ነበር፡፡ ደስታና ትዝታ ተቃረጧት፡፡ «ቀስ በቀስ ደስታዬ ውስጥ ውስጡን
እንደ እሳተ ገሞራ ፍል እየተንሸከሽከ ሰውነቴን አሞቀው፡፡ የወዲያነሽ
ጉጉትና ምኞት ተፈጸመ፡፡ ወዴት እንደሚወሰድ የማያውቀው ጋሻዬነህም
ከእናቱ ትከሻ ባሻገር ወደ ኋላ እየተመለከተ የስድስት ዓመታት መኖሪያውን ለቅቆ ወጣ፡፡
ጋሻዬነህን ይዘን ወደ ቤት ስንገባ ቀደም ብለው ወሬውን የሰሙት ሦስት ወራት ያህል የቅርብ ጎረቤቶቻችን በሙሉ ደስታ ተቀበሉን፡፡ የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አቅፋ ፊት ለፊቴ ተቀመጠች። ጋሻዬነህ ግራ ገባው። በማያውቀው አዲስ አካባቢ በመገኘቱ ተጨነቀ፡፡ ዐይኖቹ ተቅበዘበዙ፡፡ የቤቱ ዕቃና በዙሪያው ያሉት ሰዎች ሁሉ አዲስ ስለ ሆኑበት ቀስ እያለ በፍርሃት ዐይን አያቸው። የለበሰው ነጭ ልብስና የእናቲቱ አረንጓዴ ቀሚስ በአንድነት ሲታዩ በቄጠማ መኻል የበቀለች ነጭ አበባ መሰሉ፡፡ የተደረገው ውጣ ውረድ ሁሉ
አስደሰተኝ፡፡
እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ለሚመጡት የጎረቤት ሰዎች ከወዲያ ወዲህ እያሉ ጠላ የሚቀዱት ጉልላትና ሠራተኛችን ነበሩ፡፡ የወዲያነሽማ ከተቀመጠችበት የምትነሣ አትመስልም ነበር፡፡ የሰው ሁሉ ዐይን በእናትና ልጅ ላይ አረፈ። «እንኳን ለዚህ አበቃሽ! እንኳን ደስ ያላችሁ፣ እሰየው እሰይ» እያሉ የሚስሙን የሰፈሩ ሰዎች ደስታችን ደስታቸው ሆነ። ጋሻዬነህ
መላ ቅጡ ጠፋው። ከእናቱ ተቀብዬ ስታቀፈው ከጭልፊት አምልጣ ከጭራሮ
መዝጊያ ሥር እንደምትሸጎጥ ጫጩት ደረቴ ላይ ተለጠፈ፡፡ ዐሥር ሰዓት
ገደማ ጉልላት፣ እኔና የወዲያነሽ እንዲሁም የቤታችን አዲሱ 'ሰው' ብቻ
ቀረን፡፡ የቤቱን ወለል ለመንካት የፈራ ይመስል ከእኔና ከእናቱ ዕቅፍ
አልላቀቅ አለ። ካፈናት የደስታ ሲቃ ጋር ትንሽ በትንሽ ስለ ተለማመደችና
የጎጆ ነገር በመሆኑ የወዲያነሽ ጉድ ጉድ አለች፡፡ ጋሻዬነህንም በእጅዋ ይዛ
ከመኝታ ቤት ወደ ትልቁ ክፍል ከዚያም ወደ ውጭና ወደ ግቢው እየወሰደች
አዝናናችው፡፡ በፍርሃት ተሳስሮ የቆየው ሰውነቱ በመፍታታቱ በፊቱ ላይ
የፈገግታ ጮራ ታየ፡፡ የቤቱን ውስጥ ዕቃዎች አንድ በአንድ እያየ መደባበስ
ጀመረ፡፡
ከዚያም ዐልፎ ”እማማ” እያለ ጥያቄ ማቅረብ ቀጠለ፡፡ ከሁሉም ከሁሉም እማሚ የምትለዋ ቃሉ ልቤን በደስታ ዘርፍ አሳመረቻት፡፡ የጉልላትን ዐመል የምታውቀዋ የወዲያነሽ ወፍራም ሻይ አቀረበችለት፡፡ የሚፈልገውን ያህል ስላላነቃቃው ጋደም አለ፡፡ የጋሻዬነህ አእምሮ ከአካባቢው ጋር ተላምዶ ፍርሃቱ በመቃለሉ ብቻውን በሰበሰቡ ላይ መሯሯጥና ዕንጨቱን እያሻሽ መጫወት ጀመረ፡፡ ትዎትም ትም እያደረገ በፍጥነት በሚራመድበት ጊዜ አንገቴን እርሱ ወዳለበት ቦታ አስግና «ቀስ! ቀስ እያልክ እንዳትወድቅ፣ ረጋ ብለህ ነው መጫወት! እያልኩ ማስጠንቀቂያ ለመስጠት በመብቃቴ ያባትነት ኩራት ተሰማኝ፡፡ ድንገት እግሩ ከእግሩ ጋር ተጋጭቶ ወይም አንሸራቶት ሲወድቅ «አይዞህ! የኔ አንበሳ! » ብዬ ላነሳው በመሮጤ አንጎሌ
በደስታ ሰከረ፡፡ የዕለቷ ፀሐይ ግዴታዋን ጨርሳ ስትሰናበት ጉልላትንጰለመሸኘት ወጣሁ፡፡
የዚያች የጋግርታም መኪናው ሞተር ፍዳችንን አሳየን። «ሙክት ሲያጡ ወጠጤ አርደው ድግስን ይወጡ» ሆነና የእኔዋን ይዞ ሔደ፡፡ ቀኑም ሆነ ምሽቱ እንደዚያ ዕለት አጥሮብኝና ፈጥኖብኝ አያውቅም፡፡ ጊዜ የሚጨበጥ ግዙፍ ኣካል ቢሆን ኖሮ ይለይልን ነበር፡፡
አዲስ መዐድ ! በቀዳሚ ትግልና ድል ያጌጠ መዐድ! ከነጠላ ወደ ስሉስ አካላት የተሸጋገረ መዐድ! ያቺ የሁለት ቀን የወንደላጤነት ቤቴ ቀደም ሲል በየወዲያነሽ ዛሬ ደግሞ ጋሻዬነህ ደምቃ ምሰሶዋ ወፈረ።ለመጀመሪያ ጊዜ በመዐዳችን ዙሪያ ሦስት ማእዘን ሆነን ተቀመጥን። የተስፋዬ ዘለላ ተጨባጭ ፍሬ አፈራ፡፡ የመከራ ቀንበሯ ገና ያልተሰበረው የወዲያነሽ፡አረሠብሩህ ተስፋ ያለውና የሥቃይ ፍሬ የሆነው ጋሻዬነህ፣ ያን ሁሉ የኑሮ ኮረኮንች አልፈውና፡ ከፊት ለፊት ያለውን ጉራንጉራም የሕይወት ወጣ ገባ
እና የኑሮ ጭጋግ ከእኔ ጋር አብሮ ለመጋፈጥ ተገናኘን፡፡
ሕሊናችን በደስታ በመሞላቱ ሆዳችን ጠገበ፡፡ ችግር የተፈጠረው መኝታ ላይ ነበር፡፡ እኔ በበኩሌ ወደ እኔ ዞሮ አቅፌውና አቅፎኝ እንዲተኛ ስፈልግ፣ እናቱ ደግሞ «ኧረ ምን ሲደረግ አንተ እኮ አምስት ዓመት ሙሉ እስኪበቃህ አይተህ ጠግበኸዋል» ብላ አሻፈረኝ አለች፡፡ ወዲያ ብል ወዲህ ብል ተሸነፍኩ፡፡ ካንገት በላይ እሷን ያናደድኩ መስሎኝ ወደ ግድግዳው ዞሬ ተኛሁ፡፡ ዝም ብላ በመተኛት ፈንታ ቀስ እያለች ከልጅዋ ጋር ወሬዋን ቀጠለች፡፡ ትኩስ የአባትነት ቅናት አላስተኛ ስላለኝ ያለ ምክንያት መገላበጥና ማካክ አበዛሁ፡፡ የልጅዋን እጅ ባንገቷ ዙሪያ ጠምጥማ የናፍቆት ጥማቷን የምታረካዋ የወዲያነሽ «እባክህ አርፈህ ተኛ! አሁን ምን ሆንኩ ብለህ ነው
የምትገላበጠው?» አለችኝ፡፡ «አማረብኝ ብለሽ ነው? ጠቦሽ እንደሆነ ልነሣና
ልውረድ፣ አበዛሽው! » አልኩና ፍቅራዋ ቅናቴ ስለ ገነፈለብኝ «አምጪ!
አይቻልም፣ መተኛት ያለበት በእኔና በአንቺ መካከል ነው! » ብዩ አስገዳጅ
ቃላት ተናገርኩ፡፡ ከት ብላ ስቃ ጋሻዬነህን በላይዋ ላይ አሳልፋ በመካከላችን
አስተኛችው፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የሁለታችንን ክንዶች ተንተርሶ ሲተኛ ለውጡ ምን ስሜት እንደ ፈጠረበት ለማወቅ ጓጓሁ፡፡ ሙያዩ ባለመሆኑ አቃተኝ፡፡ የብልጠቴ ብልጠት ባፍንጫው በኩል የምትወጣዋን ትንፋሹን ለማዳመጥ ስል ራሱን ወደ እኔ ኣስጠጋሁት:: ጧት ግን በዕለቱ ሥራ ምክንያት ማልዳ በመነሣቷ ከጋሻዬነህ ጋር ሰፊ ልፊያና ጨዋታ ቀጠልኩ። አንዳንድ ጊዜ ወደ እኛ ዘንድ ትመጣና «በል ይውልህ! በዚህ አያያዝማ ምኑን ተነሣኸው?» ትልና ወደ ሥራዋ ትመለሳለች:: ቆየትየት ብላ ደግሞ ትመስስና «እኔ ምኑም ምኑም አልተሠራልኝም እንዳፈቀዳት አድርጋ ትሥራው:: የእናንተ ጨዋታ ናፈቀኝ» በማለት አልጋው ጫፍ ላይ እረፍ ብላ እሽቆልቁላ ትመለከተን ነበር፡፡
ያም ሆነ ይህ የጋራ ቀንዲላችን ፏ ብሉ በራ፡፡ የእኔና የወዲያነሽ የአንድነት እና የጋራ ችቦ ተንቦለቦለ፡፡ ነበልባሉ እንዳይጠፋኛ ፍሙ እንዳይከስም ፍቅራችን የነዳጅ ኃይል ሰጠው:: የሳምንቱ ቀናት እንደ ነባር አመጣጣቸው ተራ በተራ ለዘለዓለም ባለፉ ቁጥር የጋሻዬነህ ሕይወት ለውጥ ማግኘቷን ቀጠለች፡፡ «እማማዩና አባባዬ» የሚሉት ቃላት ቀስ በቀስ ተዋሐዱት፡፡ ጠባዩን ለማስተካከልና ለማረቅ እዚህ ግባ የሚባል
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ምን ብዬ እንደምጀምር ቸገረኝ፡፡ ቁርጤን ለማወቅና የምትመልስልኝን ለመስማት ያለመጠን ጓጓሁ። ከመኪናይቱ ውስጥ የመውጣት ፍላጎት ቢኖረኝም በዚያች ወቅት ረዳቴ ስለ መሰለችኝ ሙጢኝ አልኳት፡፡ ያወራነው ተራ ወሬ ሁሉ የአንጎል መርዝ ሆኖ ተሰማኝ፡፡ በመኪናይቱ ውስጥ የነበረው ሞቃት አየር እንዳይወጣ የተገዘተ ይመስል ወበቁ ፈጀን፡፡ ተነጋገርንና ከመኪናይቱ በስተምሥራቅ ኻያ እርምጃ ያህል ርቀን ተቀመጥን፡፡ እንደ ክረምት ደመና የጠቆረና የከበደ ሐሳብ አእምሮዩ ውስጥ ማንዣበቡን ቀጠለ።
ከአንድ አስፈሪ የኑሮ ገጽታ ጋር ጔተፋጠጥኩ፡፡ የጠወለገው ፊቴና በዝምታ
የተለጎመው አፌ በውስጡ አንድ ነገር እንደሚፈራገጥ ያስረዳል፡፡ ዝምታ
የሁኔታ ምልክት ነው፡፡ ጎንበስ ብዩ እንዲት እንጓ ሠርዶ አነሣሁ፡፡ አንድ
ጫፏን በፊት ጥርሴ ኣኘክሁት። የውብነሽ ዝምታዬ ስላሳሰባት «ምን ሆነሃል?
ምነው ዝም አልክ? ለዚህ ለዚህማ እዚያው እቤትህ አትጎለተውም ነበር?
ወንደላጤነት ሰለቸህ እንዴ? በጨለማ ተጻፍኖ የሚጠብቅህ ቤት አስጠላህ
መሰል?» አለችና የጥያቄ ጋጋታ አቀረበች፡፡
አነጣጥሬ መሳት ስላልፈለግሁ ከጥርጣሬና ካልባሰ ሐሳብ እንድርቅ
ፈገግ አልኩ፡፡ «ምንም አልሆንኩ እንድ ችግርና ሐሳብ ቢያጋጥመኝማ ኖሮ
እነግርሽ ነበር፡፡ እኔ የምፈራው አንቺን ሳይሆን እኔኑ ራሴን ነው። ውድቀቴንም
ሆነ ትንሣኤዬን የማፈልቀው እኔው ነኝ፡፡ ያም ሆነ ይህ ዛሬ በእኔና በአንቺ
እንድ ትልቅ ጉዳይ ያውም ሥርና ግንድ ያለው ቁም ነገር ይወጠናል።
የያዝኩትና የተለምኩት የሕይወት ጥርጊያ የልማትም ይሁን የጥፋት ፈር የሚይዘው ከእንግዲህ ወዲያ ነው፡፡ እስከ አሁን ድረስ ለመኖርና አካባቢዩን ለመምሰል ስል በምርም በቀልድም ባያሌው አታልያለሁ፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ግን
በቃኝ፡፡ ዘወትር ከማነጣጠር አንድ ቀን መተኮስ አለብኝ። ሐሳቤ ቢስማማሽም
ባይስማማሽም፣ ዘላቂ ሰላምንና ፍቅርን ቢፈጥርም ባይፈጥርም፣ ቢያቀራርበንም
ቢያራርቀንም ዛሬ ግን ይለይለት ብዩ ላብራራልሽ ቆርጬ ተነሥቻለሁ።
ሕይወቴን በማያቋርጥ የጨለማ ኦና ውስጥ ማዴፈን ስለማልፈልግ የብርሃን
ጭላንጭል ፍለጋ በምወጣበት ጊዜ እንደምትከተይኝና ረዳቴ እንደምትሆኝ
ርግጠኛ ነኝ፡፡ ጋን በጠጠር ይደገፋል ይባላል ብዬ ሐሳቤን ለማቀነባበር እና
በጥንካሪ ለመቀጠል ጥቂት ዝም አልኩ። ብዙ ሰው የራሱን ክብርና ዝና ለመጠበቅና ለማስከበር ሲል በኣካባቢው መጥፎ ባሕልና ልምድ የተለያየ በዴል
ይፈጽማል፡፡ በአሁኑ ዘመን በምድራችን ላይ አጥቂና ተጠቂ፣ የበላይና የበታች፡
ኃይለኛና ደካማ የሌለበት አካባቢ ይገኛል ብዬ አልገምትም፡፡ የጥቃት አፈፃፀሙ
ግን ያንዱ ካንዱ የተለየ ይሆናል፡፡ የእያንዳንዱ ሰው እስተሳሰቡና ዝንባሌው
ይለያይ እንጂ ኑሮን በየግል ዐይኑ ይመለከታታል፡፡ አስጨናቂና አስቸጋሪ ሁኔታ ሲያጋጥም ሰው ሁሉ ኑሮን በጋራ ዐይን የሚያይበት ጊዜ ደግሞ ይመጣል።
እናቴም ትሁን ወይም ሌላ ሰው በየዋህነት በቂና ትክክለኛ ምክንያት ነው
ብለው ባመኑበት ሁኔታ ተነሳሥተው ቢበድሉኝና ክፉ ነገር ቢፈጽሙብኝ ነገር
ግን ስሕተታቸውን ዐውቀው ካረሙ በጥፋታቸው ደረጃ መጠን ይቅርታ
አልነፍጋቸውም፡፡ የቅርብ ዘመዱ እንዳይጠቃበት ብሎ የሩቅ ወገኑን የሚያጠቃና የሚያሳድድም አለ፡፡ ራስ ወዳድነት ካጠቃው የኑሮና የሕይወት አባዜ የፈለቀ ድርጊት፣ የመፍትሔው አቅጣጫ ሌላ ነው። ስንዴ ስጥ አጠገብ ያረፈችውን ርግብ ገና ለገና ጠቅ ጠቅ ታደርግ ይሆናል በማለት በድንጋይ እንከነችራት የለ? በትምህርት ወይም በትክክለኛ የሕይወት ልምድ ያልበሰለ ሕሊና የሚሰጠው መፍትሔና ውሳኔ በስሕተትና በጥፋት የተሞላ ሊሆን ይችላል። የበሰለ ሰፊ ሕሊና ግን የሚሰጠው ውሳኔ ለምንና እንዴት እንደተሰጠ ጉዳዩን በቅድሚያ
አጢኖ ይመረምራል። ባልበሰለና ከመጥፎ እምነት ባርነት ነጻ ባልወጣ ሕሊና ላይ የሚወሰድ ማናቸውም ርምጃ በአጥጋቢና ፍትሐዊ ምርምር ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይገባል።» አልኩና እንደነገሩ ከዚህም ከዚያም አያይዤ ሰፊና ያልተጣራ የሐሳብ ዝብዝብ ካቀረብኩ በኋላ ዝምታ ጎራ ውስጥ ገባሁ፡፡ ዕቃ እንደ ጣለ ሰው ኪሴን መፈተሽ ጀመርኩ፡፡ የተናገርኩት ሁሉ ዝብርቅርቅ ያለና ግራ የሚያጋባ ስለ ሆነባት «የዛሬውስ ደግሞ የጉድ ነው፣ የተናገርከው ሁሉ አማርኛ አልመስል አለኝ፡፡ ምን ለማለት እንደ ፈለግህ ኣልገባኝም፡፡ ካልግባኝ ደግሞ መልስ ለመስጠት…» አለችና ንግግሯን ሳትጨርስ ጎንበስ ብላ ትናንሽ ጠጠሮች ለቅማ ያዘች። ሐሳቤን የምሰቀስቅበት የምክንያት ስንጥር በማጣቴ ሐሳቤ አእምሮዬ ውስጥ በጻዕር ተያዘ፡፡ በጻዕር አልኩ! እንዲያውም ሊበክት ተቃረበ። በቁሜ ተርበተበትኩ። መጀመር የመጨረስን ያህል ምንኛ አስቸጋሪ ነው? ድንገት እንደ ፈነዳ እሳተ ገሞራ የሐሳቤን ረመጥና አመድ ቋቅ አልኩት።
«በወላጆቻችን ቤት በሠራተኛነት ተቀጥራ በማገልገሏና ሠርታ በማደሯ አላፍርባትም ለወደፊትም አላፍርም» ብዬ በልበ ሙሉነት ጀመር ሳደርግ
ዐይኖቿ በድንጋጤ ቦዙ፡፡ ቀጠልኩ፡፡
የምወድሽ እኅቴ በመሆንሽ ምስጢሬን
በመሐላ አላስጠብቅሽም። በእኔ ላይ የደረሰና የሚደርስ መከራ ሁሉ ያንቺም
በመሆኑ የመከራዩ ቀንበር ተጋሪ ነሽ። እስከ ዛሬ ይህን ጉዳይ ካንቺ በመደበቄና
ሳላዋይሽም በመቅረቴ እንደ ክፉ ሰው ትቆጥሪኝ ይሆናል። ጉዙ የዋለ
መንገደኛ ሲርበው ስንቁን ይፈታል' ነውና እኔም ምቹና ትክክለኛው ጊዜ
ሲደርስና ሐሳቤ አብቦ በሚያፈራበት ወቅት ምስጢሬን ላካፍልሽ በመወሰኔ
ይኸው ዛሬ ልገልጽልሽ ነው። ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ለተናገርኩት ሐሰት
ሁሉ የእኅትነት ልቦናሽ ንጹሕ ይቅርታ አይነፍገኝም» ብዬ የሚቀጥለው
ንግግሬን ሐሳብ ለማቀነባበር ያህል ትንፋሼን ዋጥኩ። ሁለተኛዉን ምዕራፍ
ከፈትኩ። ሐሳቤን ባጭሩና በቀላሉ ለማስረዳት ስል ብዙውን የኑሮ እና የችግር ውጣ ውረድ በጥቂት ቃላት ኣጠቃለልኩት፡፡
«ከስድስት ዓመታት በፊት ያውም ይበልጣል፡ በወላጆቻችን ቤት ውስጥ
ስትሠራ የነበረችው የወዲያነሽ ብዙ ሥቃይና መከራ አሳልፋለች። ዕርጉዝ ሆና
መባረሯንም ታስታውሻለሽ፡፡ ከእኛ ቤት ተባርራ ከሄደች በኋላ ልጅ ወልዳ
በመጣሏ በወንጀለኛነት ተይዛ አምስት ዓመት ተፈረደባት። ተጥሎ የተገኘው ልጅ
አሳዳጊና ሰብሳቢ ባለማግኘቱ ለዕጓለ ማውታ ተሰጠ። አሁን ግን የእስራት ጊዜዋን ጨርሳ ከወህኒ ቤት ወጥታለች፡፡ በከባድ ችግርና በኑሮ ውጣ ውረድ በመጐሳቆሏ መልኳን እንኳ ለይቶ ስላላወቃት የገዛ አባታችን በአሁኗ ባለቤቴ ላይ አምስት ዓመት እሥራት ፈርዶባት ነበር፡፡ ሕግ የጥፋተኝነት ማረሚያ እና የኃይል ሚዛን
መለኪያና መሳያ መሣሪያ በመሆኑ የሆነው ሆኗል። የገዛ ልጄን የሙት ልጅ ነው እያልኩ በመናገሬ በርህራሄ ዐይን እንድታይው አድርጌአለሁ። አስፈላጊ ተንኮልና የልብ ማራራቂያ ዘዴ ነበር። ለየወዲያነሽ ያለኝ ፍቅር ጽኑ በመሆኑ ከወህኒ ቤት እንደ ወጣች ውድና ፍቅርት ባለቤቴ ብዬ ከእርሷ ጋር ጐጆ ወጥቻለሁ፡፡የሁለታችን የፍቅር ፍሬ የሆነውና ዕጓለ ማውታ ውስጥ ያደገው ልጃችን አሁን ከእኛ ጋር እየኖረ ነው:: ከትናንት ወዲያ በመንገድ ላይ እርሷን የምትመስል ሴት ከሩቅ አየሁ ያልሽኝም የልጀ የጋሻዬነህ እናት የማፈቅራት የኑሮ ጓደኛዬ የወዲያነሽ ነች፡፡ ባጭሩ ላጠቃልልሽ፡፡ ሦስታችንም በአንድ ላይ በመኖር ላይ ነን» ብዬ ለዓመታት በምስጢር እየቋጠርኩ ያጠራቀምኩትን ሐሳብ በደቂቃዎች ውስጥ
ዘረገፍኩላት። አንድ ግዙፍ ሽክም የተራገፈልኝ ያህል በጣም ቀለለኝ፡፡ በአካባቢዩ ያለው ነገር ሁሉ ደምቆና ፈክቶ ታየኝ፡፡ የተጠራቀመ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ምን ብዬ እንደምጀምር ቸገረኝ፡፡ ቁርጤን ለማወቅና የምትመልስልኝን ለመስማት ያለመጠን ጓጓሁ። ከመኪናይቱ ውስጥ የመውጣት ፍላጎት ቢኖረኝም በዚያች ወቅት ረዳቴ ስለ መሰለችኝ ሙጢኝ አልኳት፡፡ ያወራነው ተራ ወሬ ሁሉ የአንጎል መርዝ ሆኖ ተሰማኝ፡፡ በመኪናይቱ ውስጥ የነበረው ሞቃት አየር እንዳይወጣ የተገዘተ ይመስል ወበቁ ፈጀን፡፡ ተነጋገርንና ከመኪናይቱ በስተምሥራቅ ኻያ እርምጃ ያህል ርቀን ተቀመጥን፡፡ እንደ ክረምት ደመና የጠቆረና የከበደ ሐሳብ አእምሮዩ ውስጥ ማንዣበቡን ቀጠለ።
ከአንድ አስፈሪ የኑሮ ገጽታ ጋር ጔተፋጠጥኩ፡፡ የጠወለገው ፊቴና በዝምታ
የተለጎመው አፌ በውስጡ አንድ ነገር እንደሚፈራገጥ ያስረዳል፡፡ ዝምታ
የሁኔታ ምልክት ነው፡፡ ጎንበስ ብዩ እንዲት እንጓ ሠርዶ አነሣሁ፡፡ አንድ
ጫፏን በፊት ጥርሴ ኣኘክሁት። የውብነሽ ዝምታዬ ስላሳሰባት «ምን ሆነሃል?
ምነው ዝም አልክ? ለዚህ ለዚህማ እዚያው እቤትህ አትጎለተውም ነበር?
ወንደላጤነት ሰለቸህ እንዴ? በጨለማ ተጻፍኖ የሚጠብቅህ ቤት አስጠላህ
መሰል?» አለችና የጥያቄ ጋጋታ አቀረበች፡፡
አነጣጥሬ መሳት ስላልፈለግሁ ከጥርጣሬና ካልባሰ ሐሳብ እንድርቅ
ፈገግ አልኩ፡፡ «ምንም አልሆንኩ እንድ ችግርና ሐሳብ ቢያጋጥመኝማ ኖሮ
እነግርሽ ነበር፡፡ እኔ የምፈራው አንቺን ሳይሆን እኔኑ ራሴን ነው። ውድቀቴንም
ሆነ ትንሣኤዬን የማፈልቀው እኔው ነኝ፡፡ ያም ሆነ ይህ ዛሬ በእኔና በአንቺ
እንድ ትልቅ ጉዳይ ያውም ሥርና ግንድ ያለው ቁም ነገር ይወጠናል።
የያዝኩትና የተለምኩት የሕይወት ጥርጊያ የልማትም ይሁን የጥፋት ፈር የሚይዘው ከእንግዲህ ወዲያ ነው፡፡ እስከ አሁን ድረስ ለመኖርና አካባቢዩን ለመምሰል ስል በምርም በቀልድም ባያሌው አታልያለሁ፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ግን
በቃኝ፡፡ ዘወትር ከማነጣጠር አንድ ቀን መተኮስ አለብኝ። ሐሳቤ ቢስማማሽም
ባይስማማሽም፣ ዘላቂ ሰላምንና ፍቅርን ቢፈጥርም ባይፈጥርም፣ ቢያቀራርበንም
ቢያራርቀንም ዛሬ ግን ይለይለት ብዩ ላብራራልሽ ቆርጬ ተነሥቻለሁ።
ሕይወቴን በማያቋርጥ የጨለማ ኦና ውስጥ ማዴፈን ስለማልፈልግ የብርሃን
ጭላንጭል ፍለጋ በምወጣበት ጊዜ እንደምትከተይኝና ረዳቴ እንደምትሆኝ
ርግጠኛ ነኝ፡፡ ጋን በጠጠር ይደገፋል ይባላል ብዬ ሐሳቤን ለማቀነባበር እና
በጥንካሪ ለመቀጠል ጥቂት ዝም አልኩ። ብዙ ሰው የራሱን ክብርና ዝና ለመጠበቅና ለማስከበር ሲል በኣካባቢው መጥፎ ባሕልና ልምድ የተለያየ በዴል
ይፈጽማል፡፡ በአሁኑ ዘመን በምድራችን ላይ አጥቂና ተጠቂ፣ የበላይና የበታች፡
ኃይለኛና ደካማ የሌለበት አካባቢ ይገኛል ብዬ አልገምትም፡፡ የጥቃት አፈፃፀሙ
ግን ያንዱ ካንዱ የተለየ ይሆናል፡፡ የእያንዳንዱ ሰው እስተሳሰቡና ዝንባሌው
ይለያይ እንጂ ኑሮን በየግል ዐይኑ ይመለከታታል፡፡ አስጨናቂና አስቸጋሪ ሁኔታ ሲያጋጥም ሰው ሁሉ ኑሮን በጋራ ዐይን የሚያይበት ጊዜ ደግሞ ይመጣል።
እናቴም ትሁን ወይም ሌላ ሰው በየዋህነት በቂና ትክክለኛ ምክንያት ነው
ብለው ባመኑበት ሁኔታ ተነሳሥተው ቢበድሉኝና ክፉ ነገር ቢፈጽሙብኝ ነገር
ግን ስሕተታቸውን ዐውቀው ካረሙ በጥፋታቸው ደረጃ መጠን ይቅርታ
አልነፍጋቸውም፡፡ የቅርብ ዘመዱ እንዳይጠቃበት ብሎ የሩቅ ወገኑን የሚያጠቃና የሚያሳድድም አለ፡፡ ራስ ወዳድነት ካጠቃው የኑሮና የሕይወት አባዜ የፈለቀ ድርጊት፣ የመፍትሔው አቅጣጫ ሌላ ነው። ስንዴ ስጥ አጠገብ ያረፈችውን ርግብ ገና ለገና ጠቅ ጠቅ ታደርግ ይሆናል በማለት በድንጋይ እንከነችራት የለ? በትምህርት ወይም በትክክለኛ የሕይወት ልምድ ያልበሰለ ሕሊና የሚሰጠው መፍትሔና ውሳኔ በስሕተትና በጥፋት የተሞላ ሊሆን ይችላል። የበሰለ ሰፊ ሕሊና ግን የሚሰጠው ውሳኔ ለምንና እንዴት እንደተሰጠ ጉዳዩን በቅድሚያ
አጢኖ ይመረምራል። ባልበሰለና ከመጥፎ እምነት ባርነት ነጻ ባልወጣ ሕሊና ላይ የሚወሰድ ማናቸውም ርምጃ በአጥጋቢና ፍትሐዊ ምርምር ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይገባል።» አልኩና እንደነገሩ ከዚህም ከዚያም አያይዤ ሰፊና ያልተጣራ የሐሳብ ዝብዝብ ካቀረብኩ በኋላ ዝምታ ጎራ ውስጥ ገባሁ፡፡ ዕቃ እንደ ጣለ ሰው ኪሴን መፈተሽ ጀመርኩ፡፡ የተናገርኩት ሁሉ ዝብርቅርቅ ያለና ግራ የሚያጋባ ስለ ሆነባት «የዛሬውስ ደግሞ የጉድ ነው፣ የተናገርከው ሁሉ አማርኛ አልመስል አለኝ፡፡ ምን ለማለት እንደ ፈለግህ ኣልገባኝም፡፡ ካልግባኝ ደግሞ መልስ ለመስጠት…» አለችና ንግግሯን ሳትጨርስ ጎንበስ ብላ ትናንሽ ጠጠሮች ለቅማ ያዘች። ሐሳቤን የምሰቀስቅበት የምክንያት ስንጥር በማጣቴ ሐሳቤ አእምሮዬ ውስጥ በጻዕር ተያዘ፡፡ በጻዕር አልኩ! እንዲያውም ሊበክት ተቃረበ። በቁሜ ተርበተበትኩ። መጀመር የመጨረስን ያህል ምንኛ አስቸጋሪ ነው? ድንገት እንደ ፈነዳ እሳተ ገሞራ የሐሳቤን ረመጥና አመድ ቋቅ አልኩት።
«በወላጆቻችን ቤት በሠራተኛነት ተቀጥራ በማገልገሏና ሠርታ በማደሯ አላፍርባትም ለወደፊትም አላፍርም» ብዬ በልበ ሙሉነት ጀመር ሳደርግ
ዐይኖቿ በድንጋጤ ቦዙ፡፡ ቀጠልኩ፡፡
የምወድሽ እኅቴ በመሆንሽ ምስጢሬን
በመሐላ አላስጠብቅሽም። በእኔ ላይ የደረሰና የሚደርስ መከራ ሁሉ ያንቺም
በመሆኑ የመከራዩ ቀንበር ተጋሪ ነሽ። እስከ ዛሬ ይህን ጉዳይ ካንቺ በመደበቄና
ሳላዋይሽም በመቅረቴ እንደ ክፉ ሰው ትቆጥሪኝ ይሆናል። ጉዙ የዋለ
መንገደኛ ሲርበው ስንቁን ይፈታል' ነውና እኔም ምቹና ትክክለኛው ጊዜ
ሲደርስና ሐሳቤ አብቦ በሚያፈራበት ወቅት ምስጢሬን ላካፍልሽ በመወሰኔ
ይኸው ዛሬ ልገልጽልሽ ነው። ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ለተናገርኩት ሐሰት
ሁሉ የእኅትነት ልቦናሽ ንጹሕ ይቅርታ አይነፍገኝም» ብዬ የሚቀጥለው
ንግግሬን ሐሳብ ለማቀነባበር ያህል ትንፋሼን ዋጥኩ። ሁለተኛዉን ምዕራፍ
ከፈትኩ። ሐሳቤን ባጭሩና በቀላሉ ለማስረዳት ስል ብዙውን የኑሮ እና የችግር ውጣ ውረድ በጥቂት ቃላት ኣጠቃለልኩት፡፡
«ከስድስት ዓመታት በፊት ያውም ይበልጣል፡ በወላጆቻችን ቤት ውስጥ
ስትሠራ የነበረችው የወዲያነሽ ብዙ ሥቃይና መከራ አሳልፋለች። ዕርጉዝ ሆና
መባረሯንም ታስታውሻለሽ፡፡ ከእኛ ቤት ተባርራ ከሄደች በኋላ ልጅ ወልዳ
በመጣሏ በወንጀለኛነት ተይዛ አምስት ዓመት ተፈረደባት። ተጥሎ የተገኘው ልጅ
አሳዳጊና ሰብሳቢ ባለማግኘቱ ለዕጓለ ማውታ ተሰጠ። አሁን ግን የእስራት ጊዜዋን ጨርሳ ከወህኒ ቤት ወጥታለች፡፡ በከባድ ችግርና በኑሮ ውጣ ውረድ በመጐሳቆሏ መልኳን እንኳ ለይቶ ስላላወቃት የገዛ አባታችን በአሁኗ ባለቤቴ ላይ አምስት ዓመት እሥራት ፈርዶባት ነበር፡፡ ሕግ የጥፋተኝነት ማረሚያ እና የኃይል ሚዛን
መለኪያና መሳያ መሣሪያ በመሆኑ የሆነው ሆኗል። የገዛ ልጄን የሙት ልጅ ነው እያልኩ በመናገሬ በርህራሄ ዐይን እንድታይው አድርጌአለሁ። አስፈላጊ ተንኮልና የልብ ማራራቂያ ዘዴ ነበር። ለየወዲያነሽ ያለኝ ፍቅር ጽኑ በመሆኑ ከወህኒ ቤት እንደ ወጣች ውድና ፍቅርት ባለቤቴ ብዬ ከእርሷ ጋር ጐጆ ወጥቻለሁ፡፡የሁለታችን የፍቅር ፍሬ የሆነውና ዕጓለ ማውታ ውስጥ ያደገው ልጃችን አሁን ከእኛ ጋር እየኖረ ነው:: ከትናንት ወዲያ በመንገድ ላይ እርሷን የምትመስል ሴት ከሩቅ አየሁ ያልሽኝም የልጀ የጋሻዬነህ እናት የማፈቅራት የኑሮ ጓደኛዬ የወዲያነሽ ነች፡፡ ባጭሩ ላጠቃልልሽ፡፡ ሦስታችንም በአንድ ላይ በመኖር ላይ ነን» ብዬ ለዓመታት በምስጢር እየቋጠርኩ ያጠራቀምኩትን ሐሳብ በደቂቃዎች ውስጥ
ዘረገፍኩላት። አንድ ግዙፍ ሽክም የተራገፈልኝ ያህል በጣም ቀለለኝ፡፡ በአካባቢዩ ያለው ነገር ሁሉ ደምቆና ፈክቶ ታየኝ፡፡ የተጠራቀመ
👍5
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ወደ ወላጆቼ ቤት በሔድኩ ቁጥር መኪናዬን የማቆማት ከአካባቢው
እርቄ ነበር። በሩን እንዳንኳኳሁ ወዲያው ተከፍቶልኝ ገባሁ። በአሁኑ ጊዜ እኔና
ያ ቤት ማንና ምን መሆናችንን ዘበኛው አሳምረው አውቀውታል። ምድረ ግቢው ውስጥ ያሉት የኮክ ዛፎች፣ ኮባዎችና ሌሉቹም አትክልቶች ሁሉ የቀድሞ
ውበታቸውን የተጎናጸፉ መስለው ታዩኝ። እንድ ጊዜ ቆም ብዩ ዙሪያውን ካየሁ
በኋላ በቀጥታ ወደ ቤት ገባሁ። መመላለሱንና ወጣ ገባ ማለቱን አዘውትሬው ስለነበር ፍርሃትም ሆነ ኃፍረት አልተጠጉኝም፡፡ እሑድ እሑድ ባለነገር እንግዳ ስለማይበዛ ከአባቴ እጅ ያንዱ መልአክ መልክአ እንቶኔ አይታጣም፡፡ ግባ ስል የአባቴ ነጭ ጋቢ ቤቱን ተጨማሪ ውበት ሰጥቶታል። እናቴ የለበሰቻት ወሃ ሰማያዊ ጥለት ያላት ቀሚስ ከሩቅ ሲመለከቷት ጭጋግ የጋረደው ሰማይ ትመስላለች።
የውብነሽ በጊዜው ስለ እኔ በምታወራው ወሬ የወላጆቼ ሸካራ ስሜት ለስልሶ ውጥረቱ በመላሳቱ መሠረታዊ አስተሳሰባቸው ሳይሆን ተራ ዕለታዊ
አስተያየታቸው በመጠኑ ተለውጧል፡፡ ሁለቱም በፈገግታ ተቀበሉኝ፡፡ በሕሊናዩ
ውስጥ የለውጥ ጮራ ጨረረ፡፡ በአቀባበላቸው የተዝናናው ሕሊናዩ እጅ አነሣሰንና ሰላምታ አሰጣጤን አሳመረው:: መምጣቴን በድምፄ ያወቀችው የውብነሽ የቤት ውስጥ ቀላል ልብስ ለብሳ ከጐኔ ተቀመጠች፡፡ በውስጤ የተጠነሰሰውን ዓላማና እምነት አባቴ ፊት በዐይነ ሐሳብ አቀረብኩት። የእኔ ለጋ እምነትና የአባቴ
ግብዝ ሐሳብ ተፋጠጡ፡፡ የእኔዋ ሐሳብ በዳመራ ነበልባል ውስጥ ዘሎ ለማለፍ
እንደሚፈልግ ሰው ስትዘጋጅና የአባቴ ግትርነት በፈሪዎች መካከል እየተጎማለለ
እንደሚያሳግድ ጀግና ተኮፍሶ ታየኝ፡፡ እናቴ ፈቷን ፈታ አድርጋ ለስስ ባለ
የእናትነት ድምዕ «አረ ዛሬስ አምሮብሃል እሰየው! አባትህ እንዳለው ልብ ልትገዛ
ነው መሰል? እየተመላለስክ መጠየቁንም ሥራዬ ብለህ ይዘኸዋል፡፡ ታዲያ እንዲህ
እንዳማረብህና ሙሽራ እንደ መሰልክ ወደ ቤትህ ናና እንደ ዱሯችን ተቻችለን
አብረን እንኑር፡፡ ዕድሜ ላባትህ እንጂ ምን ጠፍቶ! ለወግ ለማረጉ ነው እንጂ
አንተም ራስህን ችለሃል። ከእንግዲህ ልጅነት የለም። እኛም እኮ እያደር...»
አለችና ንግግሯን ሳትደመድም የተገረፈ ልጅ እንደምታባብል እናት አቆላመጠችኝ
እባቴ ወለድ ለመቀበል እንዳሰፈሰፈ አራጭ ዐይን ዐይኔን እያየ መልክአ
ጊዮርጊሱን ወደ ጋቢው ውስጥ ሸጎጠና «የውብነሽማ የእኅትነቷንም እንደሆነ
አላውቅም፡፡ ነጋ ጠባ "አገኘሁት” ነጋ ጠባ እንዴት ናችሁ ብሏል፥ እንዲህ
አድርጎ፤ እንዲህ ፈጥሮ እያለች ጥሩ ጥሩህን ታወራለች እኔስ ጉቦ ሰጥተሃታል
ልበል?» አለና ያቺን በሐሰት ተጀቡና በጉቦ የምትፌጸም ነገር ሳይታወቀው
ተናግሮ ሣቀ። በእናቴ መሪነት የሚረባ የማይረባውን ስናወራ ጥቂት ደቂቃዎች
ከቆየን በኋላ አባቴ ያቺው የወንጀለኛ መቅጫ መጽሐፉ ትዝ ስላለችው ወደ
መኝታ ቤት ገባ። ግልግል አልኩ በውስጤ። ያጠራቀምኩትን ድፍረት ቀስ በቀስ ልጠቀምበት በመፈለጌ ከናቴ ጎን ተቀመጥኩ፡፡ በእኔና በእናቴ መካከል ያለው የፍቅር ገመድ በየወዲያኒሽ የተነሣ ተገዝግዞ ላላ እንጂ ፈጽሞ ባለመበጠሱ
እንደገና ለማጥበቅ አያዳግትም፡፡ እስኪ ዛሬ እንኳ እንዲህ ጠጋ ብለህ
አጫውተኝ' የእናት ወጉ ይድረሰኝ ብላ ባሸበሸበው ፊቷ ላይ ፈገግታ
ረጨችበት። ፊቷ በመጠኑ ሽብሽብ ከማለቱ በስተቀር ወዝና ሙላቱ ባለመቀነሱ መልኳ እንደ ወጣት ሴት ባይማርክም አዲስ ርጥብ ሥጋ ትመስላለች፡፡ አንገቷን ወደ ጎን ዘንበል አድርጋ ዐይን ዐይኔን እያየች እስኪ አፈር ስበላልህ ንገረኝ፡፡ ወዲያ ወዲህ ቢሉት ምንም መላ የለው፡፡ ከእኔ ከእናትህ የምትበልጥብህና አይዞህ አይሀ የምትልህን አግኝተህ እንደሆነም አትደብቀኝ፡፡ ኧረ መቼ ነው ጓዝህን
ጠቅልለህ የምትመጣው?» አለችና ከመጀመሪያው በበለጠ ትኩር ብላ ተመለከተችኝ፡፡
ከዚያች ከምወዳትና እንደ ነፍሴ ከምሳሳላት ከየወዲያነሽ ጋር ትዳር
ይዤ ንብረት መሥርቻለሁ። ምን የመሰለ ታይቶ የማይጠገብ ወንድ ልጅ ወልደናል። እሷንም በቅርብ ጊዜ ይዣት እመጣለሁ። አስታርቃችኋለሁ” ብዬ ልንገራትና ለእኔ አንድ ግልግል፣ ለእርሷ ደግሞ ያልታሰበ መርዶ በማርዳት
'ጉዷን ልየው ይሆን?” በማለት ገና ያልበሰለና ከገለባ የቀለለ ሐሳብ አሰብኩ፡፡ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ የምትጠባበቀዋ እናቴ በግራ እጅ ጣቶቿ አፏን እየተመተመች «በል እንጂ ንገረኝ? ምነው ሰምተህ ዝም አልክ?» ብላ ጥያቄዋን ደገመች። የጠየቀችኝን ትቼ ያሳለችኝን ጀመርኩ፡፡
«ለጠየቅሽኝ ጥያቄ መልስ ከመስጠቴ በፊት አንድ ነገር ብለምንሽ እሺ
ትይኛለሽ ወይ? አዎን ካልሽ እና ከማልሽልኝ እኔም ለጥያቄዎችሽ ሁሉ ደስ
በሚያሰኝ ሁኔታ እመልስልሻለሁ» ብዪ አዲስ ነገር ደቀንኩ፡፡
የእመ ብርሃን ያለህ! ደግሞ የምን ማይልኝ አመጣህ? እኔ እናትህ
ባልምልልህስ እንዴት ብዬ እንቢ እልሃለሁ፡፡ ካንተ ከልጂ የምሰስተው ምን ነገር አለና ነው?» ብላ የመሳቢያ ሐሳቧን አቀረበች፡፡ የአንደበቷ መላላት መንፈሴን
ሽምጥ ለማስጋለብ ረዳኝ፡፡ «ኧረ ለመሆኑ እኔ የምለምንሽንና የምጠይቅሽን ሁሉ
ዐይንሽን ሳታሺ ትፈጽሚልኛለሽ ወይ? ብዬ አዝማሚያዋን ለማወቅ በየዋህ መሰል አቀራረብ ስሜቷን ለመረዳት ጓጓሁ፡፡
«ልጄ ሙት አልልህም! የምትለኝን ሁሉ ባስፈለህ ጊዜ አደርግልሃለሁ፡፡ አንተ ልብ ግዛልኝ እንጂ፣ አንተን መንፈስ ቅዱስ ይጠጋህ እንጂ ለምን ባጉቼስ
አይሆንም» አለችና የልብ ልብ ሰጠችኝ፡፡ «ለመሆኑ» ብዬ ስጀምር ያን ምንም
ያልነበረበትን የቀሚሷን ጫፍ ልክ አቧራ እንደ ነካው እስመስዬ አራገፍኩና
ይህን አድርጌያለሁ፣ ይህን ፈጽሜያለሁ፣ ይህን አጥፍቻለሁ፣ የተጣሉ ወይም
የተኳረፉ ሰዎች አምጥቼ ታረቁልኝ እላለሁና፣ ታረቂልኝ ብዬ ብጠይቅሽ እሺ
ትይኛለሽ ወይ?» አልኩና ዙሪያ ጥምጥም ሄድኩ፡፡
እኔ ልሙትልህ! የምትጠይቀኝን ሁሉ እፈጽምልሃለሁ፡፡አንተ ደግሞ
በበኩልህ አባት እናቴ ቤት ብለህ ተመለስልኝ፡፡ በስተርጅና ወግ ማዕረግ አሳየኝ» ብላ ገና በመቀጠል ላይ እንዳለች ፋታ ሳልሰጥ «ምንጊዜም ብለምንሽና የፈለግሁትን ይዤ ብቀርብ ሳትቀያሚና ሳታሳፍሪ ትቀበይኛለሽ ወይ? ብዬ ውስጥ ውስጡን ለመጪው ጥቅሜ አደባሁ፡፡
የውብነሽ ጣልቃ ገብታ ወሬያችንን ባለማጨናገፏ ተደሰትኩ፡፡
«ታማኙን ወዳጄን አቡዩና!» ብላ በእምነት ፈረሷ ላይ አፈናጠጠችኝ::
«እኔ በበኩሌ ከጥቂት ቀናት በኋላ አንድ በጣም ድንቅ የሆነ ነገር ኣምጥቼ
አሳይሻለሁ» አልኩና ወደ የውብነሽ መለስ አልኩ፡፡ ልብ ለልብ በመተዋወቃችን በዐይናችን ተሣሣቅን፡፡ «እሰየው ተመስገን! አቡዩ ያውቃሉ! ምንጊዜም ረዳቴና ሰሚዩ ናቸው» ብላ እጄን ስባ ሳመችው:: ኃይለኛ ንፋስ በሌለበት ሰማይ ላይ እንደምትንሳፈፍ የማለዳ አሞራ አእምሮዬ በደስታ ተንሳፈፈች። አዝመራው ካማረልኝ የተግባር እርሻዪን ጀምሬያለሁ። የውብነሽ የወሬያችን ተካፋይ ለመሆን በመፈለጓ «አሁንስ እኔንም አስጎመዣችሁኝ የአሁኑ ፍቅራችሁስ ያጓጓል። ምነው እኔ አንድ ነገር ስለምንሽ ዓመት ሙሉ ታስደገድጊኛለሽ?» አለችና ለእኔ
የተሰጠኝን የተስፋ ቃል ሆን ብላ አጋነነችው፡፡
«አንቺ ምን ቸገረሽ ልጀ? እኔ ለስንቱ ታቦት እንደ ተሳልኩ የት አየሽና? ተማጥኜ ተማጥኜ ነው አሁንም ቢሆን ለዚህ የበቃልኝ፡፡ አንቺ ደግሞ በእኔና በልጄ መኻል ምን ጥልቅ ኣደረገሽ? የሚጠይቀኝን ሁሉ አደርግለታለሁ»
ካለች በኋላ ከደረቷ ውስጥ የምታምር አረንጓዴ መሓረብ ኣውጥታ ምንም
ጉድፍ ያልነበረባትን አፍንጫዋን ጠረገቻት፡፡
ነገር አቃኝልኝ ያልኳት ይመስል
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ወደ ወላጆቼ ቤት በሔድኩ ቁጥር መኪናዬን የማቆማት ከአካባቢው
እርቄ ነበር። በሩን እንዳንኳኳሁ ወዲያው ተከፍቶልኝ ገባሁ። በአሁኑ ጊዜ እኔና
ያ ቤት ማንና ምን መሆናችንን ዘበኛው አሳምረው አውቀውታል። ምድረ ግቢው ውስጥ ያሉት የኮክ ዛፎች፣ ኮባዎችና ሌሉቹም አትክልቶች ሁሉ የቀድሞ
ውበታቸውን የተጎናጸፉ መስለው ታዩኝ። እንድ ጊዜ ቆም ብዩ ዙሪያውን ካየሁ
በኋላ በቀጥታ ወደ ቤት ገባሁ። መመላለሱንና ወጣ ገባ ማለቱን አዘውትሬው ስለነበር ፍርሃትም ሆነ ኃፍረት አልተጠጉኝም፡፡ እሑድ እሑድ ባለነገር እንግዳ ስለማይበዛ ከአባቴ እጅ ያንዱ መልአክ መልክአ እንቶኔ አይታጣም፡፡ ግባ ስል የአባቴ ነጭ ጋቢ ቤቱን ተጨማሪ ውበት ሰጥቶታል። እናቴ የለበሰቻት ወሃ ሰማያዊ ጥለት ያላት ቀሚስ ከሩቅ ሲመለከቷት ጭጋግ የጋረደው ሰማይ ትመስላለች።
የውብነሽ በጊዜው ስለ እኔ በምታወራው ወሬ የወላጆቼ ሸካራ ስሜት ለስልሶ ውጥረቱ በመላሳቱ መሠረታዊ አስተሳሰባቸው ሳይሆን ተራ ዕለታዊ
አስተያየታቸው በመጠኑ ተለውጧል፡፡ ሁለቱም በፈገግታ ተቀበሉኝ፡፡ በሕሊናዩ
ውስጥ የለውጥ ጮራ ጨረረ፡፡ በአቀባበላቸው የተዝናናው ሕሊናዩ እጅ አነሣሰንና ሰላምታ አሰጣጤን አሳመረው:: መምጣቴን በድምፄ ያወቀችው የውብነሽ የቤት ውስጥ ቀላል ልብስ ለብሳ ከጐኔ ተቀመጠች፡፡ በውስጤ የተጠነሰሰውን ዓላማና እምነት አባቴ ፊት በዐይነ ሐሳብ አቀረብኩት። የእኔ ለጋ እምነትና የአባቴ
ግብዝ ሐሳብ ተፋጠጡ፡፡ የእኔዋ ሐሳብ በዳመራ ነበልባል ውስጥ ዘሎ ለማለፍ
እንደሚፈልግ ሰው ስትዘጋጅና የአባቴ ግትርነት በፈሪዎች መካከል እየተጎማለለ
እንደሚያሳግድ ጀግና ተኮፍሶ ታየኝ፡፡ እናቴ ፈቷን ፈታ አድርጋ ለስስ ባለ
የእናትነት ድምዕ «አረ ዛሬስ አምሮብሃል እሰየው! አባትህ እንዳለው ልብ ልትገዛ
ነው መሰል? እየተመላለስክ መጠየቁንም ሥራዬ ብለህ ይዘኸዋል፡፡ ታዲያ እንዲህ
እንዳማረብህና ሙሽራ እንደ መሰልክ ወደ ቤትህ ናና እንደ ዱሯችን ተቻችለን
አብረን እንኑር፡፡ ዕድሜ ላባትህ እንጂ ምን ጠፍቶ! ለወግ ለማረጉ ነው እንጂ
አንተም ራስህን ችለሃል። ከእንግዲህ ልጅነት የለም። እኛም እኮ እያደር...»
አለችና ንግግሯን ሳትደመድም የተገረፈ ልጅ እንደምታባብል እናት አቆላመጠችኝ
እባቴ ወለድ ለመቀበል እንዳሰፈሰፈ አራጭ ዐይን ዐይኔን እያየ መልክአ
ጊዮርጊሱን ወደ ጋቢው ውስጥ ሸጎጠና «የውብነሽማ የእኅትነቷንም እንደሆነ
አላውቅም፡፡ ነጋ ጠባ "አገኘሁት” ነጋ ጠባ እንዴት ናችሁ ብሏል፥ እንዲህ
አድርጎ፤ እንዲህ ፈጥሮ እያለች ጥሩ ጥሩህን ታወራለች እኔስ ጉቦ ሰጥተሃታል
ልበል?» አለና ያቺን በሐሰት ተጀቡና በጉቦ የምትፌጸም ነገር ሳይታወቀው
ተናግሮ ሣቀ። በእናቴ መሪነት የሚረባ የማይረባውን ስናወራ ጥቂት ደቂቃዎች
ከቆየን በኋላ አባቴ ያቺው የወንጀለኛ መቅጫ መጽሐፉ ትዝ ስላለችው ወደ
መኝታ ቤት ገባ። ግልግል አልኩ በውስጤ። ያጠራቀምኩትን ድፍረት ቀስ በቀስ ልጠቀምበት በመፈለጌ ከናቴ ጎን ተቀመጥኩ፡፡ በእኔና በእናቴ መካከል ያለው የፍቅር ገመድ በየወዲያኒሽ የተነሣ ተገዝግዞ ላላ እንጂ ፈጽሞ ባለመበጠሱ
እንደገና ለማጥበቅ አያዳግትም፡፡ እስኪ ዛሬ እንኳ እንዲህ ጠጋ ብለህ
አጫውተኝ' የእናት ወጉ ይድረሰኝ ብላ ባሸበሸበው ፊቷ ላይ ፈገግታ
ረጨችበት። ፊቷ በመጠኑ ሽብሽብ ከማለቱ በስተቀር ወዝና ሙላቱ ባለመቀነሱ መልኳ እንደ ወጣት ሴት ባይማርክም አዲስ ርጥብ ሥጋ ትመስላለች፡፡ አንገቷን ወደ ጎን ዘንበል አድርጋ ዐይን ዐይኔን እያየች እስኪ አፈር ስበላልህ ንገረኝ፡፡ ወዲያ ወዲህ ቢሉት ምንም መላ የለው፡፡ ከእኔ ከእናትህ የምትበልጥብህና አይዞህ አይሀ የምትልህን አግኝተህ እንደሆነም አትደብቀኝ፡፡ ኧረ መቼ ነው ጓዝህን
ጠቅልለህ የምትመጣው?» አለችና ከመጀመሪያው በበለጠ ትኩር ብላ ተመለከተችኝ፡፡
ከዚያች ከምወዳትና እንደ ነፍሴ ከምሳሳላት ከየወዲያነሽ ጋር ትዳር
ይዤ ንብረት መሥርቻለሁ። ምን የመሰለ ታይቶ የማይጠገብ ወንድ ልጅ ወልደናል። እሷንም በቅርብ ጊዜ ይዣት እመጣለሁ። አስታርቃችኋለሁ” ብዬ ልንገራትና ለእኔ አንድ ግልግል፣ ለእርሷ ደግሞ ያልታሰበ መርዶ በማርዳት
'ጉዷን ልየው ይሆን?” በማለት ገና ያልበሰለና ከገለባ የቀለለ ሐሳብ አሰብኩ፡፡ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ የምትጠባበቀዋ እናቴ በግራ እጅ ጣቶቿ አፏን እየተመተመች «በል እንጂ ንገረኝ? ምነው ሰምተህ ዝም አልክ?» ብላ ጥያቄዋን ደገመች። የጠየቀችኝን ትቼ ያሳለችኝን ጀመርኩ፡፡
«ለጠየቅሽኝ ጥያቄ መልስ ከመስጠቴ በፊት አንድ ነገር ብለምንሽ እሺ
ትይኛለሽ ወይ? አዎን ካልሽ እና ከማልሽልኝ እኔም ለጥያቄዎችሽ ሁሉ ደስ
በሚያሰኝ ሁኔታ እመልስልሻለሁ» ብዪ አዲስ ነገር ደቀንኩ፡፡
የእመ ብርሃን ያለህ! ደግሞ የምን ማይልኝ አመጣህ? እኔ እናትህ
ባልምልልህስ እንዴት ብዬ እንቢ እልሃለሁ፡፡ ካንተ ከልጂ የምሰስተው ምን ነገር አለና ነው?» ብላ የመሳቢያ ሐሳቧን አቀረበች፡፡ የአንደበቷ መላላት መንፈሴን
ሽምጥ ለማስጋለብ ረዳኝ፡፡ «ኧረ ለመሆኑ እኔ የምለምንሽንና የምጠይቅሽን ሁሉ
ዐይንሽን ሳታሺ ትፈጽሚልኛለሽ ወይ? ብዬ አዝማሚያዋን ለማወቅ በየዋህ መሰል አቀራረብ ስሜቷን ለመረዳት ጓጓሁ፡፡
«ልጄ ሙት አልልህም! የምትለኝን ሁሉ ባስፈለህ ጊዜ አደርግልሃለሁ፡፡ አንተ ልብ ግዛልኝ እንጂ፣ አንተን መንፈስ ቅዱስ ይጠጋህ እንጂ ለምን ባጉቼስ
አይሆንም» አለችና የልብ ልብ ሰጠችኝ፡፡ «ለመሆኑ» ብዬ ስጀምር ያን ምንም
ያልነበረበትን የቀሚሷን ጫፍ ልክ አቧራ እንደ ነካው እስመስዬ አራገፍኩና
ይህን አድርጌያለሁ፣ ይህን ፈጽሜያለሁ፣ ይህን አጥፍቻለሁ፣ የተጣሉ ወይም
የተኳረፉ ሰዎች አምጥቼ ታረቁልኝ እላለሁና፣ ታረቂልኝ ብዬ ብጠይቅሽ እሺ
ትይኛለሽ ወይ?» አልኩና ዙሪያ ጥምጥም ሄድኩ፡፡
እኔ ልሙትልህ! የምትጠይቀኝን ሁሉ እፈጽምልሃለሁ፡፡አንተ ደግሞ
በበኩልህ አባት እናቴ ቤት ብለህ ተመለስልኝ፡፡ በስተርጅና ወግ ማዕረግ አሳየኝ» ብላ ገና በመቀጠል ላይ እንዳለች ፋታ ሳልሰጥ «ምንጊዜም ብለምንሽና የፈለግሁትን ይዤ ብቀርብ ሳትቀያሚና ሳታሳፍሪ ትቀበይኛለሽ ወይ? ብዬ ውስጥ ውስጡን ለመጪው ጥቅሜ አደባሁ፡፡
የውብነሽ ጣልቃ ገብታ ወሬያችንን ባለማጨናገፏ ተደሰትኩ፡፡
«ታማኙን ወዳጄን አቡዩና!» ብላ በእምነት ፈረሷ ላይ አፈናጠጠችኝ::
«እኔ በበኩሌ ከጥቂት ቀናት በኋላ አንድ በጣም ድንቅ የሆነ ነገር ኣምጥቼ
አሳይሻለሁ» አልኩና ወደ የውብነሽ መለስ አልኩ፡፡ ልብ ለልብ በመተዋወቃችን በዐይናችን ተሣሣቅን፡፡ «እሰየው ተመስገን! አቡዩ ያውቃሉ! ምንጊዜም ረዳቴና ሰሚዩ ናቸው» ብላ እጄን ስባ ሳመችው:: ኃይለኛ ንፋስ በሌለበት ሰማይ ላይ እንደምትንሳፈፍ የማለዳ አሞራ አእምሮዬ በደስታ ተንሳፈፈች። አዝመራው ካማረልኝ የተግባር እርሻዪን ጀምሬያለሁ። የውብነሽ የወሬያችን ተካፋይ ለመሆን በመፈለጓ «አሁንስ እኔንም አስጎመዣችሁኝ የአሁኑ ፍቅራችሁስ ያጓጓል። ምነው እኔ አንድ ነገር ስለምንሽ ዓመት ሙሉ ታስደገድጊኛለሽ?» አለችና ለእኔ
የተሰጠኝን የተስፋ ቃል ሆን ብላ አጋነነችው፡፡
«አንቺ ምን ቸገረሽ ልጀ? እኔ ለስንቱ ታቦት እንደ ተሳልኩ የት አየሽና? ተማጥኜ ተማጥኜ ነው አሁንም ቢሆን ለዚህ የበቃልኝ፡፡ አንቺ ደግሞ በእኔና በልጄ መኻል ምን ጥልቅ ኣደረገሽ? የሚጠይቀኝን ሁሉ አደርግለታለሁ»
ካለች በኋላ ከደረቷ ውስጥ የምታምር አረንጓዴ መሓረብ ኣውጥታ ምንም
ጉድፍ ያልነበረባትን አፍንጫዋን ጠረገቻት፡፡
ነገር አቃኝልኝ ያልኳት ይመስል
👍3👏2
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...እናቴ ደረጃው ላይ ቆማ «አደራ በጊዜ እንድትመለሺ... ይኽ ወጣ ወጣ..» አለቻትና ተመልሳ ገባች። የቀኑ ሞቃት አየር እንደ ብረት ምጣድ ያሰማትን መኪና ከፍተን በቀጥታ ጉዞ ጀመርን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከቤቴ አጥር በር አጠገብ ስንደርስ በደከሙ ዓይኖቹ ትናንሽ ፊደሉች እንደሚያነብ ዓይነ ደካማ ሽማግሌ፣ የውብነሽ በድንጋጤና በመገረም ዐይኗን ተክላ አየችኝ፡፡
«ያንተ ነገር እኮ አይታወቅም፡ ደረስን ልትለኝ እኮ ይሆናል» ብላ ወረቱ እንደ ረከሰበት ነጋደ ዐይኗ ቃበዘ፡፡ እጆቿ ተወራጩ፡፡ ቁልቁልም ሽቅብም
ወሰደቻቸው:: መጨረሻዋን ለማየት በጸጥታ ተቀመጥኩ፡፡ ቃላቷ በድንጋጤ
እየተቆራረጡ «እንዴት ብዩ ዐይኗን አየዋለሁ? ስንገናኝ ምን ምን ልበላት? በዚያ በሥቃይና መከራዋ ጊዜ ሳልጠይቃትና የት ገባች ሳልላት ኖሬ አሁን እንዲህ ብቅ ስል ምን ትለኛለች? ወይኔ ዛሬ 0ፈር በበላሁት!» አለችና ያንን ምድረ በዳ የሆነ ዐይኗን አቁለጨለጨችው::
«ይልቅ ነይ እንሒድ! እንዳንድ ጊዜ እዚህ ድረስ እየመጣች
ስለምትቀበለኝ አጉል ቦታ ላይ እንዳታገኝኽና ይብሱን እንዳትርበተበቺ ብዩ ከመናገሬ ጋሻዬነህ ከወደ ቤት «እባብዪ መጣ አባባ መጣ! » እያለ ሲጮህ ተሰማ፡፡ እናቱ ደግሞ በዚያች ቀጠን ብላ ቃናዋ በሚማርክ ድምጺ ና! ና
ተመለስ! ተው ትወድቃለህ! » እያለች ስትጣራና ስታስጠነቅቅ ሰማን። የውብነሽ
ማንቁርቱን እንቀው ዐይኑን እንዳስፈጠጡት ሰው አይኗ ፈጠጠ። የየወዲያነሽን ድምፅ ከሰማች ድፍን ስድስት ዓመት ኣልፏል። የውብነሽን ለማበረታታት ያህል
«አይዞሽ አትፍሪ! » ባለቤቴ እኮ ክፉ ሰው አይደለችም፡፡ ገና ገባ ስንል አንገቷ
ላይ ተጠምጥመሽ ሳሚያትና ኃፍረትሽን አስወግጂ፡፡ እንደገና ደግሞ ሳሚያት።
በእርሷ በኩል ሁሉንም ነገር በይቅርታ ትታዋለች፡፡ ከትናንት ጀምራ በጉጉት ነው
የምትጠባበቅሽ» አልኩና ከዚህም ከዚያም እምታትቼ እበረታታኋት፡፡ መለስ
ያለውን የአጥር በር ከፍተን ገባን።
ጋሻዬነህ ሰብሰቡ ሳይ ዝንጉርጉር ኳስ እያንከባለለ ይጫወት ነበር፡፡ ኳሱን
ጥሉ እየሮጠ መጥቶ አጠገቤ እንደደረሰ እጁን ዘረጋ፡፡ ቅብል ብዬ ታቀፍኩት፡፡
የየውብነሽ አእምሮ ያለ የሌለ ኃይሉን ፍርሃትን ለመቋቋሚያ አዋለው:: ዐይኖቿ
እንኳ በሚገባ ማየት የሚችሉ አይመስሉም ነበር፡፡ ቀይ ዳማ ፊቷ ከረመጥ የወጣ ካራ መስሎ ለሥቃይ መግለጫ ትሆን ዘንድ የተቀረፀች የመብ ሐውልት መሰለች፡፡ ወደ ቤት ገባ እንዳልን የወዲያነሽ ከወደ ጓዳ ወጣች፡፡ ባለ ወይን ጠጅ ጥለት ሽንሽን ቀሚስና ብሩህ እረንጓዴ እጀ ጉርድ ሹራብ ለብሳለች፡፡ ጸጉሯን በቀላሉ ጐንጉናና የቤት ውስጥ ቀላል ጫማ እድርጋ ወደ እኔ ስትመጣ
ከበስተጀርባዬ ያለችውን የውብነሽን ከወደ ጎኔ በኩል ኣየቻት። «እውይ የውብነሽ! አቤት የውቧ !» ብላ እጅዋን እስከ ትከሸዋ ከፍ ኣድርጋ ተንደርድራ
አንገቷ ላይ ተጠመጠመች። የየውብነሽ ኮሮጆ በድንጋጤም ይሁን ከደስታ ብዛት
አምልጧት ወደቀ፡፡ እንስቼ ወንበር ላይ አስቀመጥኩት። ተቃቅፈው ሲሳሳሙ
ልክየለሽ ደስታ አጥለቀለቀኝ፡፡ የምሆነው መላቅጡ ጠፋኝ፡፡ የየወዲያነሽ አለባበስ
እንደ ነገሩ ቢሆንም ደስ አለኝ እንጂ አልተከፋሁም። ጎን ለጎን ተቀምጠው
«ደኅና ነሽ ወይ?» እየተባባሉ በሣቅና በፈግታ ሲጠያየቁ ምንጊዜም በቃላት
እቀናብሬ ልገልጸው የማይቻለኝ ደስታ ተሰማኝ፡፡ ጋሻዬነህ ጭኔ ላይ አስቀምጬ
ፊት ለፊታቸው ጉብ አልኩ፡፡ ደቂቃዎች እየፈነጠዙ ተግተለተሉ፡፡ የየውብነሽ
ፍርሃትና ድንጋጤ ሙልጭ ብሎ ከላይዋ ላይ በመጥፋቱ ያለቻትን ፈገግታ ሁሉ
ሞጣጥጣ አወጣቻት። ጋሻዬነህ ከጭኔ ላይ ወርዶ ወደ እናቱ ሲሔድ የውብነሽ
አገላብጣ ሳመችው። ዐይን ዐይኑን እያየች «እንኳን ለዚህ አበቃችሁ እኔንም
እንኳን ይህን ለማየት አበቃኝ» ብላ ኣንስታ አቀፈችው::
የወዲያነሽን፡ ስለ የውብነሽ እንግድነት ይህን ይህን እንድታዘጋጂ ብዬ አልነገርኳትም። ደስ የሚያሰኘውንና መቅረብ የሚገባውን ነገር ሁሉ
ስለምታውቀው ይህን እንድትሠሪ ያንን እንዳትረሺ ማለት አላስፈለገኝም፡፡
የወዲያነሽ ንብ ነች! የውብነሽ አሁንም
አሁንም የማርያምን ጽዋ እያስቆሙ
እንደሚስሙ ሕፃናት የጋሻዬነህን ጉንጭ ደጋግማ ሳመች። ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ
እውነተኛ ድል ከድሉች ሁሉ የበለጠ ድል ነው። የወዲያነሽ ግልጽና ቅን ከመሆኗ
የተነሣ ከየውብነሽ ጋር በምትነጋገርበት ጊዜ ሁሉ ካንጀቷ ስለምትሥቅና ፈገግ
ስለምትል አኳኋኗና አቀራረቧ ሁሉ የየውብነሽን ልብ ማረከው፡፡ ቀድሞም ቢሆን የውብነሽና የወዲያነሽ በጣም ይዋደዱ ስለነበር አሁን ከጥቂት ዓመታት በኋላ ሲገናኙ ፍቅራቸው ከትዝታቸው ሰታቴ ገንፍሎ ወጣ፡፡ የሁለቱ መግባባትና አዲስ ግንኙነት መጀመር ለእኔ አንድ ታላቅ የትግል ምርት ነበር። በእኅቴና በባለቤቴ መካከል ያለው ጋሻዬነህም በሁለት የሚያማምሩ አበቦች ዙሪያ እንደምትዞር የመስቀል ወፍ ይማርካል። የወዲያነሽ ከሁለታችን ተለይታ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
በጋሻዬነህና በአክስቱ እንዲሁም በእኔ መካከል ውብ ትዝታው እስከ መቼም የማይረሳ ወሬ ቀጠለ፡፡ ጊዜ እንደ አበደ ውሻ ተክለፈለፈች። መሰለኝ እንጂ አትረዝም አታጥር! የወዲያነሽ ከሠራተኛይቱ ጋር በመረዳዳት ምግብና
መጠጥ አቀረቡ። ከግምቴ በላይ ሆኖ በማግኘቴ በአቀራረቧ ረክቼ ባይኔ ጠገብኩ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ እኔ፤ ባለቤቴና እኅቴ በአንድ ማዕድ ዙሪያ ቀረብን፡፡ ድሉ ግን የእኔና የየወዲያዩ ነበር፡፡ ምንም እንኳ የውብነሽን ያ በአእምሮዋ ውስጥ
ተዳፍኖ በመጥፎ ትዝታ የሚጫረው ያንድ ቀን ስሕተቷ እያጸጸተ አንገቷን
እንድትደፋ ቢታገላትም እጅግም ስላላጠቃት ጨዋታው ደራ፡፡ የወዲያነሽ
በተደጋጋሚ ስታጎርሳት ቀጥ ያለ ዓቀበት ዘልቆ እፎይ እንዳለ መንገደኛ ተደሰትኩ፡፡ የውብነሽም በሌላ በኩል ብድር የምትመልስ ይመስል «ይቺን ብቻ
ጋሻው» እያለች ለጋሻዬነህ ታጎርሳለች፡፡
የማዕዱ ጣጣ ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ መኝታ ቤቴ ገባሁ፡፡ እንደ ልብ
እንዲጠያየቁና እንዲጫወቱ ነጻነት መስጠቴ ነበር፡፡ ተቆርጦ እንደ ወደቀ የጥድ ዕንጨት ተዘረርኩ እንጂ እንቅልፍስ በዐይኔም አልተኳለ፡፡
የፈለግኸውን ነገር ብትጠይቀኝና አድርጊልኝ ብትለኝ እፈጽምልሃለሁ፡
የፈለግሁትን ሰው አምጥቼ ታረቁልኝ ብል እታረቅልሃለሁ ብለሽኛልና በይ
እንግዲህ እንደ መሐላሽና እንደ ቃልሽ ፈፅሚልኝ ብዬ እናቴን ሳስገድዳት እሺ
ብላ የወዲያነሽ ጋር ትታረቅልኛለች ወይ?» የሚለው ሓሳብ አንጎሌን በሥጋት
ሹል ወስፌ ዉቀዉቀው። ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄዎች ደረደርኩ፡፡
እናቴ በአስገዳጅ ምክንያቶችና ሁኔታዎች ተገፋፍታ እሺ ብትለኝና ከባለቤቴ ጋር ብትታረቅልኝ የአባቴን ጉዳይ እንዴት ልወጣው እችላለሁ? የሚለው ሐሳብ ደግሞ የባሕር ላይ ኩበት አደረገኝ። ይህ ጉዳይ በእናቴ በኩል ቢደርሰው ይቀላል ወይስ በቀጥታ በእኔ አማካይነት? ይሁን ፈጽሞ ያላወቀውንና ይደርሳል ብሎ ያልጠረጠረውን ነገር ከሥር ከመሠረቱ አብራርቶ ለማስረዳት ቀላሉ ዘዴ ምንድነው? እያልኩ ራስን በራሲ በሐሳብ ቢላዋ ዘለከልኩት።
በቀላል ሐሳብም ሆነ በጊዜያዊ መግባባት ከአባቴ ይልቅ እናቴ ቅረብ
ስለምትለኝ በመጀመሪያ በእናቴ በኩል ያለውን ወደ ፍጻሚ ማድረስ አለብኝ
የሚለው ሐሳብ አመዘነ፡፡ በሐሳብ አዞሪት ውስጥ ተዘፍቄ ብቅ ጥልቅ በማለት ላይ
እንዳለው የውብነሽ ጋሻዬነህን
ስትገባ ከአሳቢ ተናጠብኩ፡፡
አልተንቀሳቀስኩም፡፡ ጎንበስ ብላ ጫማውን ካወለቀችለት በኋላ በላዩ ሳይ አሻግሬ አልጋው ላይ አስቀመችው::
ትንሽ ጎበጥ ብላ በሁለት እጅዋ አልጋውን በመመርኮዝ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...እናቴ ደረጃው ላይ ቆማ «አደራ በጊዜ እንድትመለሺ... ይኽ ወጣ ወጣ..» አለቻትና ተመልሳ ገባች። የቀኑ ሞቃት አየር እንደ ብረት ምጣድ ያሰማትን መኪና ከፍተን በቀጥታ ጉዞ ጀመርን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከቤቴ አጥር በር አጠገብ ስንደርስ በደከሙ ዓይኖቹ ትናንሽ ፊደሉች እንደሚያነብ ዓይነ ደካማ ሽማግሌ፣ የውብነሽ በድንጋጤና በመገረም ዐይኗን ተክላ አየችኝ፡፡
«ያንተ ነገር እኮ አይታወቅም፡ ደረስን ልትለኝ እኮ ይሆናል» ብላ ወረቱ እንደ ረከሰበት ነጋደ ዐይኗ ቃበዘ፡፡ እጆቿ ተወራጩ፡፡ ቁልቁልም ሽቅብም
ወሰደቻቸው:: መጨረሻዋን ለማየት በጸጥታ ተቀመጥኩ፡፡ ቃላቷ በድንጋጤ
እየተቆራረጡ «እንዴት ብዩ ዐይኗን አየዋለሁ? ስንገናኝ ምን ምን ልበላት? በዚያ በሥቃይና መከራዋ ጊዜ ሳልጠይቃትና የት ገባች ሳልላት ኖሬ አሁን እንዲህ ብቅ ስል ምን ትለኛለች? ወይኔ ዛሬ 0ፈር በበላሁት!» አለችና ያንን ምድረ በዳ የሆነ ዐይኗን አቁለጨለጨችው::
«ይልቅ ነይ እንሒድ! እንዳንድ ጊዜ እዚህ ድረስ እየመጣች
ስለምትቀበለኝ አጉል ቦታ ላይ እንዳታገኝኽና ይብሱን እንዳትርበተበቺ ብዩ ከመናገሬ ጋሻዬነህ ከወደ ቤት «እባብዪ መጣ አባባ መጣ! » እያለ ሲጮህ ተሰማ፡፡ እናቱ ደግሞ በዚያች ቀጠን ብላ ቃናዋ በሚማርክ ድምጺ ና! ና
ተመለስ! ተው ትወድቃለህ! » እያለች ስትጣራና ስታስጠነቅቅ ሰማን። የውብነሽ
ማንቁርቱን እንቀው ዐይኑን እንዳስፈጠጡት ሰው አይኗ ፈጠጠ። የየወዲያነሽን ድምፅ ከሰማች ድፍን ስድስት ዓመት ኣልፏል። የውብነሽን ለማበረታታት ያህል
«አይዞሽ አትፍሪ! » ባለቤቴ እኮ ክፉ ሰው አይደለችም፡፡ ገና ገባ ስንል አንገቷ
ላይ ተጠምጥመሽ ሳሚያትና ኃፍረትሽን አስወግጂ፡፡ እንደገና ደግሞ ሳሚያት።
በእርሷ በኩል ሁሉንም ነገር በይቅርታ ትታዋለች፡፡ ከትናንት ጀምራ በጉጉት ነው
የምትጠባበቅሽ» አልኩና ከዚህም ከዚያም እምታትቼ እበረታታኋት፡፡ መለስ
ያለውን የአጥር በር ከፍተን ገባን።
ጋሻዬነህ ሰብሰቡ ሳይ ዝንጉርጉር ኳስ እያንከባለለ ይጫወት ነበር፡፡ ኳሱን
ጥሉ እየሮጠ መጥቶ አጠገቤ እንደደረሰ እጁን ዘረጋ፡፡ ቅብል ብዬ ታቀፍኩት፡፡
የየውብነሽ አእምሮ ያለ የሌለ ኃይሉን ፍርሃትን ለመቋቋሚያ አዋለው:: ዐይኖቿ
እንኳ በሚገባ ማየት የሚችሉ አይመስሉም ነበር፡፡ ቀይ ዳማ ፊቷ ከረመጥ የወጣ ካራ መስሎ ለሥቃይ መግለጫ ትሆን ዘንድ የተቀረፀች የመብ ሐውልት መሰለች፡፡ ወደ ቤት ገባ እንዳልን የወዲያነሽ ከወደ ጓዳ ወጣች፡፡ ባለ ወይን ጠጅ ጥለት ሽንሽን ቀሚስና ብሩህ እረንጓዴ እጀ ጉርድ ሹራብ ለብሳለች፡፡ ጸጉሯን በቀላሉ ጐንጉናና የቤት ውስጥ ቀላል ጫማ እድርጋ ወደ እኔ ስትመጣ
ከበስተጀርባዬ ያለችውን የውብነሽን ከወደ ጎኔ በኩል ኣየቻት። «እውይ የውብነሽ! አቤት የውቧ !» ብላ እጅዋን እስከ ትከሸዋ ከፍ ኣድርጋ ተንደርድራ
አንገቷ ላይ ተጠመጠመች። የየውብነሽ ኮሮጆ በድንጋጤም ይሁን ከደስታ ብዛት
አምልጧት ወደቀ፡፡ እንስቼ ወንበር ላይ አስቀመጥኩት። ተቃቅፈው ሲሳሳሙ
ልክየለሽ ደስታ አጥለቀለቀኝ፡፡ የምሆነው መላቅጡ ጠፋኝ፡፡ የየወዲያነሽ አለባበስ
እንደ ነገሩ ቢሆንም ደስ አለኝ እንጂ አልተከፋሁም። ጎን ለጎን ተቀምጠው
«ደኅና ነሽ ወይ?» እየተባባሉ በሣቅና በፈግታ ሲጠያየቁ ምንጊዜም በቃላት
እቀናብሬ ልገልጸው የማይቻለኝ ደስታ ተሰማኝ፡፡ ጋሻዬነህ ጭኔ ላይ አስቀምጬ
ፊት ለፊታቸው ጉብ አልኩ፡፡ ደቂቃዎች እየፈነጠዙ ተግተለተሉ፡፡ የየውብነሽ
ፍርሃትና ድንጋጤ ሙልጭ ብሎ ከላይዋ ላይ በመጥፋቱ ያለቻትን ፈገግታ ሁሉ
ሞጣጥጣ አወጣቻት። ጋሻዬነህ ከጭኔ ላይ ወርዶ ወደ እናቱ ሲሔድ የውብነሽ
አገላብጣ ሳመችው። ዐይን ዐይኑን እያየች «እንኳን ለዚህ አበቃችሁ እኔንም
እንኳን ይህን ለማየት አበቃኝ» ብላ ኣንስታ አቀፈችው::
የወዲያነሽን፡ ስለ የውብነሽ እንግድነት ይህን ይህን እንድታዘጋጂ ብዬ አልነገርኳትም። ደስ የሚያሰኘውንና መቅረብ የሚገባውን ነገር ሁሉ
ስለምታውቀው ይህን እንድትሠሪ ያንን እንዳትረሺ ማለት አላስፈለገኝም፡፡
የወዲያነሽ ንብ ነች! የውብነሽ አሁንም
አሁንም የማርያምን ጽዋ እያስቆሙ
እንደሚስሙ ሕፃናት የጋሻዬነህን ጉንጭ ደጋግማ ሳመች። ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ
እውነተኛ ድል ከድሉች ሁሉ የበለጠ ድል ነው። የወዲያነሽ ግልጽና ቅን ከመሆኗ
የተነሣ ከየውብነሽ ጋር በምትነጋገርበት ጊዜ ሁሉ ካንጀቷ ስለምትሥቅና ፈገግ
ስለምትል አኳኋኗና አቀራረቧ ሁሉ የየውብነሽን ልብ ማረከው፡፡ ቀድሞም ቢሆን የውብነሽና የወዲያነሽ በጣም ይዋደዱ ስለነበር አሁን ከጥቂት ዓመታት በኋላ ሲገናኙ ፍቅራቸው ከትዝታቸው ሰታቴ ገንፍሎ ወጣ፡፡ የሁለቱ መግባባትና አዲስ ግንኙነት መጀመር ለእኔ አንድ ታላቅ የትግል ምርት ነበር። በእኅቴና በባለቤቴ መካከል ያለው ጋሻዬነህም በሁለት የሚያማምሩ አበቦች ዙሪያ እንደምትዞር የመስቀል ወፍ ይማርካል። የወዲያነሽ ከሁለታችን ተለይታ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
በጋሻዬነህና በአክስቱ እንዲሁም በእኔ መካከል ውብ ትዝታው እስከ መቼም የማይረሳ ወሬ ቀጠለ፡፡ ጊዜ እንደ አበደ ውሻ ተክለፈለፈች። መሰለኝ እንጂ አትረዝም አታጥር! የወዲያነሽ ከሠራተኛይቱ ጋር በመረዳዳት ምግብና
መጠጥ አቀረቡ። ከግምቴ በላይ ሆኖ በማግኘቴ በአቀራረቧ ረክቼ ባይኔ ጠገብኩ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ እኔ፤ ባለቤቴና እኅቴ በአንድ ማዕድ ዙሪያ ቀረብን፡፡ ድሉ ግን የእኔና የየወዲያዩ ነበር፡፡ ምንም እንኳ የውብነሽን ያ በአእምሮዋ ውስጥ
ተዳፍኖ በመጥፎ ትዝታ የሚጫረው ያንድ ቀን ስሕተቷ እያጸጸተ አንገቷን
እንድትደፋ ቢታገላትም እጅግም ስላላጠቃት ጨዋታው ደራ፡፡ የወዲያነሽ
በተደጋጋሚ ስታጎርሳት ቀጥ ያለ ዓቀበት ዘልቆ እፎይ እንዳለ መንገደኛ ተደሰትኩ፡፡ የውብነሽም በሌላ በኩል ብድር የምትመልስ ይመስል «ይቺን ብቻ
ጋሻው» እያለች ለጋሻዬነህ ታጎርሳለች፡፡
የማዕዱ ጣጣ ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ መኝታ ቤቴ ገባሁ፡፡ እንደ ልብ
እንዲጠያየቁና እንዲጫወቱ ነጻነት መስጠቴ ነበር፡፡ ተቆርጦ እንደ ወደቀ የጥድ ዕንጨት ተዘረርኩ እንጂ እንቅልፍስ በዐይኔም አልተኳለ፡፡
የፈለግኸውን ነገር ብትጠይቀኝና አድርጊልኝ ብትለኝ እፈጽምልሃለሁ፡
የፈለግሁትን ሰው አምጥቼ ታረቁልኝ ብል እታረቅልሃለሁ ብለሽኛልና በይ
እንግዲህ እንደ መሐላሽና እንደ ቃልሽ ፈፅሚልኝ ብዬ እናቴን ሳስገድዳት እሺ
ብላ የወዲያነሽ ጋር ትታረቅልኛለች ወይ?» የሚለው ሓሳብ አንጎሌን በሥጋት
ሹል ወስፌ ዉቀዉቀው። ሌሎችም ተመሳሳይ ጥያቄዎች ደረደርኩ፡፡
እናቴ በአስገዳጅ ምክንያቶችና ሁኔታዎች ተገፋፍታ እሺ ብትለኝና ከባለቤቴ ጋር ብትታረቅልኝ የአባቴን ጉዳይ እንዴት ልወጣው እችላለሁ? የሚለው ሐሳብ ደግሞ የባሕር ላይ ኩበት አደረገኝ። ይህ ጉዳይ በእናቴ በኩል ቢደርሰው ይቀላል ወይስ በቀጥታ በእኔ አማካይነት? ይሁን ፈጽሞ ያላወቀውንና ይደርሳል ብሎ ያልጠረጠረውን ነገር ከሥር ከመሠረቱ አብራርቶ ለማስረዳት ቀላሉ ዘዴ ምንድነው? እያልኩ ራስን በራሲ በሐሳብ ቢላዋ ዘለከልኩት።
በቀላል ሐሳብም ሆነ በጊዜያዊ መግባባት ከአባቴ ይልቅ እናቴ ቅረብ
ስለምትለኝ በመጀመሪያ በእናቴ በኩል ያለውን ወደ ፍጻሚ ማድረስ አለብኝ
የሚለው ሐሳብ አመዘነ፡፡ በሐሳብ አዞሪት ውስጥ ተዘፍቄ ብቅ ጥልቅ በማለት ላይ
እንዳለው የውብነሽ ጋሻዬነህን
ስትገባ ከአሳቢ ተናጠብኩ፡፡
አልተንቀሳቀስኩም፡፡ ጎንበስ ብላ ጫማውን ካወለቀችለት በኋላ በላዩ ሳይ አሻግሬ አልጋው ላይ አስቀመችው::
ትንሽ ጎበጥ ብላ በሁለት እጅዋ አልጋውን በመመርኮዝ
👍3🥰1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...«አባባ ትላንት ከሰዓት በኋላ ሔደ፡፡ ከሳምንት በላይ ይቆያል፡፡ሲያተራምስ ነው የሚሰነብተው:: ያሰብነው ጉዳይ እንደፈለግነው ሊፈጸም ይችላል ማለት ነው» አለች የውብነሽ ቅዳሜ ማለዳ በቁርስ ሰዓት የምሥራች ነው
የምትለውን ወሬ እያወራች፡፡
ለግብግቤ አንድ ተጨማሪ ርምጃ እንደሚሆን በማመኔ ደስ አለኝ።
ጠረጴዛውን ተደግፋ ወደ ቆመችው ባለቤቴ ዞር አልኩና ዛሬ ጋሻዬነህ አብሮኝ
ለቁርቁስ የሚሔድበት ቀን በመሆኑ አደይ አበባ እስመስለሽው ቆይኝ፣ የሚያምርበትን ልብስ አንቺ ታውቂዋለሽ፡፡ ወዴት እንደሚሄድና ጉዳዩ ምን እንደሆነ ነግሬሻለሁ» ብዬ ወደ ውስጥ ገባሁ፡፡ ልክ እንደ እዲስ ወፈፌ ያቅበዝብዝ
ያዘኝ፡፡ “ጭንቅላት በደስታ ሲሰክር! ለብሼ ስመለስ እኅቴና ባለቤቴ ወሬያቸውን
ተያይዘውታል፡፡ አልተጋራኋቸውም፡፡ መኪናይቱን እስከማሟሙቅ ድረስ ደረሱብኝ፡፡መንገድ ስንጀምር የወዲያነሽ ተመለሰች። «የውብነሽ፣ ሰባት ሰዓት ሲሆን እዚሁ ጠብቂኝ» ብያት ከመሥሪያ ቤቷ በር ላይ ተመለስኩ፡፡ የሥራ መግቢያ ሰዓት ሞልቶ ስለ ነበር ሠራተኛው በሙሉ ነጠላና ጥንድ ሆኖ እያውካካ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ገና ቁጭ ከማለቴ ቅናት እንደሚያንዘፈዝፈው ሰው መላ አካላቴ እየተንቀጠቀጠ አወከኝ፡፡ በአካባቢዬ ያለው ዕቃ ሁለ ጥያቄ የሚያቀርብልኝ እየመሰለኝ ”እስቲ አባክ! አንድ ቃል ይውጣህ! እንደሚል ሰው እጉርጩ አየሁት።
በጦርነት ዋዜማ እንደምትሸበር የፈሪ ልብ የልቤ ትርታ ከገደቡ በላይ ናረ፡፡ ለቆላ ቁስል የሆድ ቁርጠት መድኃነት መዋጥ ሆነብኝ፡፡ ብናኝ የምታህል የመንፈስ ጸጥታ ሳላገኝ ቀረሁ። የሰዓቴን ጠቋሚ ዘንግ ወደፊት በማስኬድ የጊዜን
ሥርዓታዊ ጉዞ ለመለወጥ ያስችለኝ ይመስል ሦስት ከኻያ የነበረውን አራት ከኻያ አደረግሁት፡፡ራሴን በማጭበርበሬና ሕሊናዬን በታለሌ ረቂቅ ኃፍረት ተሰማኝና
መልሼ አስተካከልኳት። እርሳሱ፣ ወረቀቱ፣ ብዕሩ፣ ወንበርና ጠረጴዛዉ ደመኛዩ
መሰሉኝ፡፡ ሒድ ሒድ ውጣ ውጣ የሚል ነገር ያዘኝ። በቀጥታ አለቃዬ ቢሮ ገባሁ፡፡
አእምሮው ተቃውሶ ሁኔታዎችን እንደ ዘነጋ ሰው ከፊታቸው ተገተርኩ፡፡ ቀና
ብለው ሲያዩኝ «ዛሬ በጣም አሞኛል ምናልባት ቢሻለኝ ብዬ ነበር የመጣሁት።
እያመመኝ ከመቀመጥ ብሄድ ይሻላል» አልኩና በዙሪያዬ የውሸት ገረገራ አጠርኩ።አለቃዩ ዘለው ለመግባት አልቻሉም። ካመመሕማ ሂድ፣ በጎ ካልሆንክ ደግሞ ሰኞ ሰው ላክ» አለና ያስደስተዋል ብለው ያሰቡትን በሞኝ ሰው ፊት ላይ የሚታይ የፈገግታ ዐይነት አቀረቡልኝ፡፡ ልቤ በደስታ ከመነረቱ የተነሣ ሣቄ ፈንድቶ አጉል እንዳያደርገኝ ነገር ሳላበዛ አመስግኜ ሹልክ አልኩ፡፡
ጭንቀትና ሥጋት ተንጠርዞ እንደ ከበደኝ በመኪናዩ ገሠገሥኩ። በራሴ
ለመተማመን ያልቻልኩበትን ምክንያት ፈልፍዬ ማውጣት ባለመቻሌ በውስጡ
ትልቅ ችግር ተፈጠረ። ከመኪናዬ ወርጄ ወደ ቤት ስራመድ ምንና የት
እንደምረግጥ የማውቅ አልመስልም። ማንም ሳያየኝ ሰተት ብዬ እንግዳ መቀበያ
ክፍላችንም ገባሁ፡፡ በቀስታ ሄጄ ከመስተዋቱ ፊት ለፊት ቆምኩ። አኳኋኔ
ስላላስደሰተኝ ምናልባት በፈገግታ ቢለወጥልኝ ብዬ ፈገግ አልኩ። ከውስጥ
ያልመነው ፈገግታ በመሆኑ ወዲያው ከሰመ፡፡ እንዲያውም ስካሩ ያልበረደለት
ሰው መሰልኩ እንጂ ጤነኛውን ጌታነህን ለመሆን አልቻልኩም፡፡ ከወደ መኝታ
ቤት እየኮረኮሩ የሚያሥት የልጅ ሣቅ አሁንም አሁንም ይሰማል። ወዲያው
ከሚከታተሉትና ሊይዙት ከተዘረጉት እጆች ለማምለጥ ግማሽ ኃይሉን ለሣቅ ያዋለ
ልጅ ከወደጓዳ እየሮጠ መጣ። ከእኔ ራቅ ብሉ ድካም የዋጣት ሣቅ እየሣቀ ቆመ፡፡
አላየኝም። የወዲያነሽ ጥቂት ዘግየት ብላ ጫጩቷን ተከትላ እንደምትሄድ ዶሮ
እሱን ለመያዝ እየሮጠች መጣች።
በልፊያ የተበታተነው ጸጉሯ እንደ ጋሽበ አዝመራ የራሱን ግላዊ ውበት ፈጥሯል። በዚያች ሰዓት ወደ ቤት ይመለሳል ብለው ስለማይጠረጥሩ እናትና ልጅ አላዩኝም፡፡ ፊቷ እንደ በጋ ወራት ሙሉ ጨረቃ ደምቆ «መጣሁብህ! ያዝኩህ!» ብላ ወደ እርሱ ተራመደች፡፡
በመሮጥ ፈንታ ሆዱን ወደ ውስጥ እጥፍ ሣቁን ለቀቀው። አፈፍ አደረገችው:: ከቡችላዋ ጋር እንደምትላፋ እናቲት ወሻ ጎበስ ብላ ወገቡን ያዘችውና ትግል ገጠሙ:: ከወዲያ ወዲህ አባተለችው፡፡ የጋሻዬነህ ሣቅ ገነነች፡፡ ትርዒቱ እንዲቀጥል እንጂ እንዲቋረጥ ባለመፈለጌ እንደ ምሰሶ ጸጥ ብዩ
ተገተርኩ፡፡ ወደ ላይ እንሥታ አንጋጣ ስትመለከተው ውብ ጥርሶቿ ተፈለቀቁ፡፡
ስለ ከበዳት አወረደችው:: ወለሉ ላይ ስታቆመው ጸጉሯን በጣቶቹ በተነባት፡፡
ሲናከሱና ሲናጩ ውለው እንደ ደከሙ አውራ ዶሮዎች እናትና ልጅ ፊት ለፊት
ቆመው ተያዩ። ጋሻዬነህ በአጋጣሚ እኔ ወዳለሁበት ዐይኑን መለስ ሲያደርግ
ድንገት አየኝና «አባብዬ! » ብሉ በሩጫ መጥቶ እግሬ ላይ ተጠመጠመ፡፡
አንሥቼ ታቀፍኩት፡፡ የወጂያነሽ ባደረገችው ልፊያ ፍቅራዊ ኃፍረት ስለ ተሰማት ከበስተጀርባዬ ቆማ አንገቴ ላይ ተጠመጠመች፡፡ በአፍንጫዋ በኩል የሚወጣው ትንፋሽ እየተናጠች እንደምትስቅ ያስታውቃል። ወደ መስታወቱ ላይ የፊተኛው ጨምዳዳ ገጽታዩ ጠፍቶ በአዲስ ፈገግታ ተተክቷል። ከግራናከቀኝ አማከለውኝ ተቀመጡ፡፡ ያ ሲያዋክበኝ የነበረው ጭንቀት ለጊዜው ገለል ስላለልኝ ጥቂት ተዝናናሁ፡፡ . የጋሻዩነህ ወለላ አንደበትና የየወዲያነሽ ለዛሚ ቃላት አያረኩኝ አምስት ተኩል ሆነ። ከዚያ በኋላ ግን እሷ ወደ ማድ ቤት፣ ልጃችን ከቤት ውጪ ወጣ፡፡ ወጣ ከማለታቸው ሥጋትና ጭንቀት ተቃረጡኝ:: እንቅልፍ የሥጋትን
እድፍ አጥቦ ይወስድልኝ ይመስል ገብቼ ጋደም አልኩ፡፡ ዳሩ ግን አስጨናቂ
ሐሳብ ከጣራው ላይ የተንጠባጠበ ያህል ልዩ ልዩ ሐሳብ እንደ ጉንዳን ወረረኝ።
ታገልኩት፡፡ በመጨረሻ ግን «ዛሬ ድል ማድረግ አለብኝ የሕሊናዩ ትክክለኛ ወኔ
መገንፈል አለበት። ምንም እንኳ ከንትርክ ይልቅ መግባባት ለመቀራረቢያ የተሻለ
ቢሆንም ዛሬ ደግሞ አንድ ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ሰፊ የኑሮ ምዕራፍ
የምደመድምበት ቀን ነው» አልኩ፡፡ አእምሮዬ ጥቂት ሰከን በማለቱ ለዐርባ
ደቂቃ ያህል ደህና እንቅልፍ ወሰደኝ። ከሩቅ የሚሰማው የኤሌትሪክ እምቢልታ
በወፍራሙ ጀምሮ በቀጭኑ በመዉረስ ሰባት ሰዓት መሙላቱን አሰማ፡፡ የጋለ ሽቦ
እንዳ ነካው ሰው ደንግጬ ተነሳሁ። እመር ብዬ ወርጄ ጫማዬን አደረግሁና ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ገባሁ፡፡ ለካስ የውብነሽ ቀደም ብላ ገብታ ኖሮ የውጪ
አገር መጽሔት እያገላበጠች ተዝናንታ ትጠብቀኛለች፡፡ አንዳችም ሐሳብና ሥጋት
ያለባት አትመስልም፡፡
ከምሳ በኋላ የአለባበስ ችሎታዬን ሁሉ አጠቃልዩ በዕለቱ አለባበሴ ላይ
አዋልኩት፡፡ ሙሽራ ሆኜ ባላውቅም ሙሽራ መሰልኩ። አንጎሌ የኑሮ ፈተናውን
ውጤት ለማየት አሰፈሰፈ። የወዲያነሽ የመሄጃችን ጊዜ መዳረሱን በማወቋ
ጋሻዬነህን ይዛ ወደ መኝታ ቤት ገባች፡፡ አሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ
አጥቢያ ኮከብ አስመስላው መጣች። በእኔና በየውብነሽ ዝምታ ጭር ብሎ
የነበረው ክፍል በጋሻነህ የልብስ ውበት እንደገና ነፍስ ዘራ፡፡
«በሉ እንግዲህ በርቱ ይኸውላችሁ! ይቅናችሁ! አድባር ትቀበላችሁ ነው
የሚባለው» ብላ አስረከበችን፡፡ «ጨክነሽ?» አልኳት የምትለውን ለመስማት። ከዚህ አልፈ ምን ለማለት እችላለሁ በሚል አስተያየት አየችኝ። የውብነሽ ጋሻዩነህን ይዛ ፊት ለፊቴ ቆመች፡፡ ልማደኛው ሐሳቤ ተመሳቀለ፡፡ እኔንና ልጄን ወደ ሰው አለባ ምድረበዳ የምትገፈትረን መሰለኝ፡፡
«ተነሥ እንጂ ምን ትጠብቃለህ» ተባልኩ፡፡ በድካም እንደ ተጠቃ ሰው
በዝግታ ተነሣሁ።
የመጨረሻው ግብ ግብ የመጀመሪያው ምዕራፍ ተከፈተ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...«አባባ ትላንት ከሰዓት በኋላ ሔደ፡፡ ከሳምንት በላይ ይቆያል፡፡ሲያተራምስ ነው የሚሰነብተው:: ያሰብነው ጉዳይ እንደፈለግነው ሊፈጸም ይችላል ማለት ነው» አለች የውብነሽ ቅዳሜ ማለዳ በቁርስ ሰዓት የምሥራች ነው
የምትለውን ወሬ እያወራች፡፡
ለግብግቤ አንድ ተጨማሪ ርምጃ እንደሚሆን በማመኔ ደስ አለኝ።
ጠረጴዛውን ተደግፋ ወደ ቆመችው ባለቤቴ ዞር አልኩና ዛሬ ጋሻዬነህ አብሮኝ
ለቁርቁስ የሚሔድበት ቀን በመሆኑ አደይ አበባ እስመስለሽው ቆይኝ፣ የሚያምርበትን ልብስ አንቺ ታውቂዋለሽ፡፡ ወዴት እንደሚሄድና ጉዳዩ ምን እንደሆነ ነግሬሻለሁ» ብዬ ወደ ውስጥ ገባሁ፡፡ ልክ እንደ እዲስ ወፈፌ ያቅበዝብዝ
ያዘኝ፡፡ “ጭንቅላት በደስታ ሲሰክር! ለብሼ ስመለስ እኅቴና ባለቤቴ ወሬያቸውን
ተያይዘውታል፡፡ አልተጋራኋቸውም፡፡ መኪናይቱን እስከማሟሙቅ ድረስ ደረሱብኝ፡፡መንገድ ስንጀምር የወዲያነሽ ተመለሰች። «የውብነሽ፣ ሰባት ሰዓት ሲሆን እዚሁ ጠብቂኝ» ብያት ከመሥሪያ ቤቷ በር ላይ ተመለስኩ፡፡ የሥራ መግቢያ ሰዓት ሞልቶ ስለ ነበር ሠራተኛው በሙሉ ነጠላና ጥንድ ሆኖ እያውካካ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ገና ቁጭ ከማለቴ ቅናት እንደሚያንዘፈዝፈው ሰው መላ አካላቴ እየተንቀጠቀጠ አወከኝ፡፡ በአካባቢዬ ያለው ዕቃ ሁለ ጥያቄ የሚያቀርብልኝ እየመሰለኝ ”እስቲ አባክ! አንድ ቃል ይውጣህ! እንደሚል ሰው እጉርጩ አየሁት።
በጦርነት ዋዜማ እንደምትሸበር የፈሪ ልብ የልቤ ትርታ ከገደቡ በላይ ናረ፡፡ ለቆላ ቁስል የሆድ ቁርጠት መድኃነት መዋጥ ሆነብኝ፡፡ ብናኝ የምታህል የመንፈስ ጸጥታ ሳላገኝ ቀረሁ። የሰዓቴን ጠቋሚ ዘንግ ወደፊት በማስኬድ የጊዜን
ሥርዓታዊ ጉዞ ለመለወጥ ያስችለኝ ይመስል ሦስት ከኻያ የነበረውን አራት ከኻያ አደረግሁት፡፡ራሴን በማጭበርበሬና ሕሊናዬን በታለሌ ረቂቅ ኃፍረት ተሰማኝና
መልሼ አስተካከልኳት። እርሳሱ፣ ወረቀቱ፣ ብዕሩ፣ ወንበርና ጠረጴዛዉ ደመኛዩ
መሰሉኝ፡፡ ሒድ ሒድ ውጣ ውጣ የሚል ነገር ያዘኝ። በቀጥታ አለቃዬ ቢሮ ገባሁ፡፡
አእምሮው ተቃውሶ ሁኔታዎችን እንደ ዘነጋ ሰው ከፊታቸው ተገተርኩ፡፡ ቀና
ብለው ሲያዩኝ «ዛሬ በጣም አሞኛል ምናልባት ቢሻለኝ ብዬ ነበር የመጣሁት።
እያመመኝ ከመቀመጥ ብሄድ ይሻላል» አልኩና በዙሪያዬ የውሸት ገረገራ አጠርኩ።አለቃዩ ዘለው ለመግባት አልቻሉም። ካመመሕማ ሂድ፣ በጎ ካልሆንክ ደግሞ ሰኞ ሰው ላክ» አለና ያስደስተዋል ብለው ያሰቡትን በሞኝ ሰው ፊት ላይ የሚታይ የፈገግታ ዐይነት አቀረቡልኝ፡፡ ልቤ በደስታ ከመነረቱ የተነሣ ሣቄ ፈንድቶ አጉል እንዳያደርገኝ ነገር ሳላበዛ አመስግኜ ሹልክ አልኩ፡፡
ጭንቀትና ሥጋት ተንጠርዞ እንደ ከበደኝ በመኪናዩ ገሠገሥኩ። በራሴ
ለመተማመን ያልቻልኩበትን ምክንያት ፈልፍዬ ማውጣት ባለመቻሌ በውስጡ
ትልቅ ችግር ተፈጠረ። ከመኪናዬ ወርጄ ወደ ቤት ስራመድ ምንና የት
እንደምረግጥ የማውቅ አልመስልም። ማንም ሳያየኝ ሰተት ብዬ እንግዳ መቀበያ
ክፍላችንም ገባሁ፡፡ በቀስታ ሄጄ ከመስተዋቱ ፊት ለፊት ቆምኩ። አኳኋኔ
ስላላስደሰተኝ ምናልባት በፈገግታ ቢለወጥልኝ ብዬ ፈገግ አልኩ። ከውስጥ
ያልመነው ፈገግታ በመሆኑ ወዲያው ከሰመ፡፡ እንዲያውም ስካሩ ያልበረደለት
ሰው መሰልኩ እንጂ ጤነኛውን ጌታነህን ለመሆን አልቻልኩም፡፡ ከወደ መኝታ
ቤት እየኮረኮሩ የሚያሥት የልጅ ሣቅ አሁንም አሁንም ይሰማል። ወዲያው
ከሚከታተሉትና ሊይዙት ከተዘረጉት እጆች ለማምለጥ ግማሽ ኃይሉን ለሣቅ ያዋለ
ልጅ ከወደጓዳ እየሮጠ መጣ። ከእኔ ራቅ ብሉ ድካም የዋጣት ሣቅ እየሣቀ ቆመ፡፡
አላየኝም። የወዲያነሽ ጥቂት ዘግየት ብላ ጫጩቷን ተከትላ እንደምትሄድ ዶሮ
እሱን ለመያዝ እየሮጠች መጣች።
በልፊያ የተበታተነው ጸጉሯ እንደ ጋሽበ አዝመራ የራሱን ግላዊ ውበት ፈጥሯል። በዚያች ሰዓት ወደ ቤት ይመለሳል ብለው ስለማይጠረጥሩ እናትና ልጅ አላዩኝም፡፡ ፊቷ እንደ በጋ ወራት ሙሉ ጨረቃ ደምቆ «መጣሁብህ! ያዝኩህ!» ብላ ወደ እርሱ ተራመደች፡፡
በመሮጥ ፈንታ ሆዱን ወደ ውስጥ እጥፍ ሣቁን ለቀቀው። አፈፍ አደረገችው:: ከቡችላዋ ጋር እንደምትላፋ እናቲት ወሻ ጎበስ ብላ ወገቡን ያዘችውና ትግል ገጠሙ:: ከወዲያ ወዲህ አባተለችው፡፡ የጋሻዬነህ ሣቅ ገነነች፡፡ ትርዒቱ እንዲቀጥል እንጂ እንዲቋረጥ ባለመፈለጌ እንደ ምሰሶ ጸጥ ብዩ
ተገተርኩ፡፡ ወደ ላይ እንሥታ አንጋጣ ስትመለከተው ውብ ጥርሶቿ ተፈለቀቁ፡፡
ስለ ከበዳት አወረደችው:: ወለሉ ላይ ስታቆመው ጸጉሯን በጣቶቹ በተነባት፡፡
ሲናከሱና ሲናጩ ውለው እንደ ደከሙ አውራ ዶሮዎች እናትና ልጅ ፊት ለፊት
ቆመው ተያዩ። ጋሻዬነህ በአጋጣሚ እኔ ወዳለሁበት ዐይኑን መለስ ሲያደርግ
ድንገት አየኝና «አባብዬ! » ብሉ በሩጫ መጥቶ እግሬ ላይ ተጠመጠመ፡፡
አንሥቼ ታቀፍኩት፡፡ የወጂያነሽ ባደረገችው ልፊያ ፍቅራዊ ኃፍረት ስለ ተሰማት ከበስተጀርባዬ ቆማ አንገቴ ላይ ተጠመጠመች፡፡ በአፍንጫዋ በኩል የሚወጣው ትንፋሽ እየተናጠች እንደምትስቅ ያስታውቃል። ወደ መስታወቱ ላይ የፊተኛው ጨምዳዳ ገጽታዩ ጠፍቶ በአዲስ ፈገግታ ተተክቷል። ከግራናከቀኝ አማከለውኝ ተቀመጡ፡፡ ያ ሲያዋክበኝ የነበረው ጭንቀት ለጊዜው ገለል ስላለልኝ ጥቂት ተዝናናሁ፡፡ . የጋሻዩነህ ወለላ አንደበትና የየወዲያነሽ ለዛሚ ቃላት አያረኩኝ አምስት ተኩል ሆነ። ከዚያ በኋላ ግን እሷ ወደ ማድ ቤት፣ ልጃችን ከቤት ውጪ ወጣ፡፡ ወጣ ከማለታቸው ሥጋትና ጭንቀት ተቃረጡኝ:: እንቅልፍ የሥጋትን
እድፍ አጥቦ ይወስድልኝ ይመስል ገብቼ ጋደም አልኩ፡፡ ዳሩ ግን አስጨናቂ
ሐሳብ ከጣራው ላይ የተንጠባጠበ ያህል ልዩ ልዩ ሐሳብ እንደ ጉንዳን ወረረኝ።
ታገልኩት፡፡ በመጨረሻ ግን «ዛሬ ድል ማድረግ አለብኝ የሕሊናዩ ትክክለኛ ወኔ
መገንፈል አለበት። ምንም እንኳ ከንትርክ ይልቅ መግባባት ለመቀራረቢያ የተሻለ
ቢሆንም ዛሬ ደግሞ አንድ ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ሰፊ የኑሮ ምዕራፍ
የምደመድምበት ቀን ነው» አልኩ፡፡ አእምሮዬ ጥቂት ሰከን በማለቱ ለዐርባ
ደቂቃ ያህል ደህና እንቅልፍ ወሰደኝ። ከሩቅ የሚሰማው የኤሌትሪክ እምቢልታ
በወፍራሙ ጀምሮ በቀጭኑ በመዉረስ ሰባት ሰዓት መሙላቱን አሰማ፡፡ የጋለ ሽቦ
እንዳ ነካው ሰው ደንግጬ ተነሳሁ። እመር ብዬ ወርጄ ጫማዬን አደረግሁና ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ገባሁ፡፡ ለካስ የውብነሽ ቀደም ብላ ገብታ ኖሮ የውጪ
አገር መጽሔት እያገላበጠች ተዝናንታ ትጠብቀኛለች፡፡ አንዳችም ሐሳብና ሥጋት
ያለባት አትመስልም፡፡
ከምሳ በኋላ የአለባበስ ችሎታዬን ሁሉ አጠቃልዩ በዕለቱ አለባበሴ ላይ
አዋልኩት፡፡ ሙሽራ ሆኜ ባላውቅም ሙሽራ መሰልኩ። አንጎሌ የኑሮ ፈተናውን
ውጤት ለማየት አሰፈሰፈ። የወዲያነሽ የመሄጃችን ጊዜ መዳረሱን በማወቋ
ጋሻዬነህን ይዛ ወደ መኝታ ቤት ገባች፡፡ አሥር ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ
አጥቢያ ኮከብ አስመስላው መጣች። በእኔና በየውብነሽ ዝምታ ጭር ብሎ
የነበረው ክፍል በጋሻነህ የልብስ ውበት እንደገና ነፍስ ዘራ፡፡
«በሉ እንግዲህ በርቱ ይኸውላችሁ! ይቅናችሁ! አድባር ትቀበላችሁ ነው
የሚባለው» ብላ አስረከበችን፡፡ «ጨክነሽ?» አልኳት የምትለውን ለመስማት። ከዚህ አልፈ ምን ለማለት እችላለሁ በሚል አስተያየት አየችኝ። የውብነሽ ጋሻዩነህን ይዛ ፊት ለፊቴ ቆመች፡፡ ልማደኛው ሐሳቤ ተመሳቀለ፡፡ እኔንና ልጄን ወደ ሰው አለባ ምድረበዳ የምትገፈትረን መሰለኝ፡፡
«ተነሥ እንጂ ምን ትጠብቃለህ» ተባልኩ፡፡ በድካም እንደ ተጠቃ ሰው
በዝግታ ተነሣሁ።
የመጨረሻው ግብ ግብ የመጀመሪያው ምዕራፍ ተከፈተ፡፡
👍5
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ከወደ ጋራው አካባቢ እሪታና ዋይታ ተሰማ፡፡ “ኡ! ኡ!.ኡ.!! የሀገር ያለህ! የመንግሥት ያለህ! የወገን ያለህ! ኡ.ኡ.ኡ. እሪ!” የሚሉ ሰዎች ቁጥራቸው እየተበራከተ ሄደና የህብረት ጩኸታቸውን ያቀልጡት ጀመር፡፡
የመንደሪቱ ነዋሪዎች ዱላ የያዘ ዱላውን ጠመንጃ ያለው ጠመንጃውን እያነሳ የተጣደፈው ባዶ እጁን ለእርዳታ ወደ ዋይታና እሪታው ቦታ ገስገስ በተፈጠረው ድርጊት በመደናገጥ የበለጠ የሰው ሀይል ለማስባሰብ ተኩስ ተተኮስ፡፡
“ቷ! ቷ! . ዷ! ዷ! ህፃናትና ሴቶች ሲቀሩ ሌላው ግልብጥ ብሎ ወጥቶ አካባቢውን አጣበበው። ድርጊቱ እጅግ የሚያስደነግጥ ፍፁም ዐይን ሊያምነው የማይችል ጆሮ ቢሰማው የሚሰቀጥጥ ሆነ፡፡ የዚህ አይነቱ ወንጀል ለብዙ ሰዎች አዲስ ከመሆኑም ሌላ ወንጀሉ የተፈፀመበት ሰው ገበየሁ መሆኑ ደግሞ ህዝቡን እርስ በርሱ አባለው። አንጫጫው። ቀድሞ እዚያ የደረስው ጭንቅላቱን ይዞ “
እግዚኦ! እግዚኦ! ያንተ ያለህ!” እያለ አንዱ
በሌላው ላይ እየዘለለ ያየው ነገር አስደንግጦት ድርጊቱ አስበርግጎት
ቁጣው ከስማይ እንደወረደ ሁሉ ወደ ስማይ ያንጋጥጣል፡፡ መልካም ባህሪ የነበረው ትህትናው ለአንድ ቀን እንኳን ተጓድሎ የማያውቀው ስሙ በክፉ ተነስቶ የማያውቀው ገበየሁ፣ ለትዳሩ ቀና ደፋ የሚለው ገበየሁ፣ ትዳሩ ለሌሎች ምሳሌነት የሚበቃው ገበየሁ የዚህ አይነቱ አስቃቂ ዕጣ ፈንታ ደርሶበት በጫካ ውስጥ ተደፍቶ ይቀራል ብሎ ማመን እጅግ አስቸጋሪ ሆነባቸው፡፡ መሞቱን የሚጠራጠሩ በፍፁም እሱ ሊሆን አይችልም በማለት የሚከራከሩም አልጠፉም ነበር፡፡ ወዲያና ወዲህ ተሯሩጠው ከብቶቹ መዘረፋቸውን ሲያረጋግጡ ግን ከብቶቹን ለመዝረፍ
በመጣ ወንበዴ እጅ የተገደለ እሱ ራሱ ገበየሁ መሆኑን ሳይወዱ በግድ
እያመኑ መጡ፡፡
“እባካችሁ ጎበዝ! እባካችሁ እስቲ ቶሎ ቶሎ ብላችሁ ቅደሙ! ትኩስ ደም ላይ ከደረሰች ልክፍት ነው የሚገድላት! ድንጋጤው ሰው አያደርጋትም!
እባካችሁ ወደ ቤት እሩጡ! ጉዷን ያላወቀች ወደዚሁ እየመጣች ይሆናል
ዋ! እቴን! እሪታው የቤቷ ጉድ መሆኑን ሳታውቅ ድንገት ደሙ ላይ እንዳትቆምና እንዳትጎዳ ፍጠኑ!” አለ አንዱ የቅርብ ጎረቤት ዓላሚቱ እሪታውን ሰምታ እንዳትመጣ እየሰጋ፡፡
“ጎበዝ! ምናልባት ተጠራጥራ ካስቸገረቻችሁ በጉልበትም ቢሆን ይዛችሁ አቆዩአት። ከሞት ታድነው ደሙ ላይ ደርሳ እንዳትለከፍ! አጉል ራሷን
አደጋ ላይ እንዳትጥል ተጠንቀቁ!” ሲሉ ሌላው ጎረቤት አክለው አሳሰቡ፡፡
በዚሁ መሰረት ደህና ደህና ጡንቻ ያላቸው ስድስት ጎረምሶች ወደ ገበየሁ መኖሪያ ቤት ሮጡ፡፡ ዓለሚቱ ምን እንደተፈጠረ ምን በመፈጠር ላይ እንዳለ ቀድማ አውቃዋለች።ባሏ ከብቶቹን ለግጦሽ ካሰማራበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን ሁኔታ ጠንቅቃ ታውቃለች። ጎንቻ እንደፎከረ ያደረገው መሆኑን የተረዳችው ገበየሁ ከብቶቹ እንዲታለቡ ወደ ቤት ይዟቸው
የሚመለስበት ሰዓት ሲያልፍ ነበር፡፡
የተፈፀመውን ድርጊት ፍፁም እንዳላወቀች ሆና ተጨንቃ ሰው ካላስጨነቀች በስተቀር ሀሜትና አሉባልታው እንደማያስቀምጣት ስለምታውቅ ተዘጋጀች።
ተከታትለው የደረሱትን ወንዶች በጭንቀት መልክ እያስተዋለች... እንዴ! ምነው?! ምንድነው? እንዴ! ምን ተፈጠረ?! ገበየሁ ደህና አይደለም እንዴ!? ወየው ጉዴ! ኸረ ባካችሁ ንገሩኝ?! ምንድነው ግርግሩ?!
ጨኸት…የምን ጩኸት ነው? ወየው! ኸረ ዘንድሮ! እኔ እኮ ሲዘገይብኝ ነው ልቤ የነገረኝ ኸረ! ኡኡ ኡ በዚህ ጊዜ ወንዶቹ የምታብድና ራሷን የምትገድል ስለመሰላቸው ደንግጠው ከግራና ቀኝ ሁለቱንም እጆችዋን አፈፍ ፣አፈፍ አድርገው ያዟት። በዚህ ጊዜ ለየላት። እንባዋ ግድቡን እንደ ጣሰ ጎርፍ መንታ መንታ ሆኖ እየተንዶለዶላ በጥፍሯም በንክሻም የተሰበሰበውን ሰው ሁሉ ትፈጀው ጀመር። ጠቅላላ ቤቱን ቀበሮ የገባበት የበግ መንጋ አስመሰለችው። አተራመሰችው። በዚህ ቅፅበት ወዳጅ ጎረቤቱ መጀመሪያ ቤቷን ከዚያም ቀስ በቀስ ደጁን እየሞላው መጣ፡፡
የቅርብ ዘመድ የሆነው ኡኡታውን እዬዬና ዋይታውን ከርቀት እያስማ መጉረፍ ጀመረ። “ዓለሚቱ ጉድ ሆን! ዓላምዬ እጃችን ተቆረጠ! ዓለምዬ ጉድ ፈላ! ውሽታሙ ገበየሁ! አታላዩ ገበየሁ! ልጆችህን ሳትሰናበት ገበየሁ! እሪ” እያለ ከአንጀቱ አለቀሰ፡፡ ዓለሚቱም ለያዥ ለገናዥ እስከምታስቸግር ድረስ እየጮኽች ደረቷን ደለቀች፡፡ያንን አስደናቂ የማስመሰል ችሎታዋን የታዘበ ሰው የዓለሚቱን እንከን የለሽ መሪ የፊልም ተዋናይነት ያለ አንዳች ጥርጥር ይመሰክርላታል፡፡ ያንን የተዋጣለት ድራማ ሰርታ ካጠናቀቀችና የሚስኪኑ ገበየሁ አሟሟት ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጎ አስከሬኑ አሰላ ከተማ ሆስፒታል ተወስዶ ከተመረመረ በኋላ በተወለደ በሰላሳ
ሶስተኛ ዓመት ዕድሜው ወደ ዘለዓለማዊ ቤቱ ወደ መቃብር ወረደ።
“ቤቴን ትዳሬን ልጆቼን ሚስቴን” እንዳለ ሳያስበው እንደወጣ ቀረ። መሪር ሀዘንና የማይጠፋ ፀፀትን በወላጆቹና በወዳጅ ዘመዶቹ ልብ ውስጥ ጥሎ አለፈ... ዓለሚቱ ሀዘኑ ያደከማት፣ የደቆሳት መሰለች።
“ከእንግዲህ ጠንከር በይ እንጂ ዓለሚቱ? ከዚህ በላይ ራስሽን መጉዳት የለብሽም፡፡ ራስሽን ከዚህ በላይ ጎድተሽ እነዚህ ልጆች ሜዳ ላይ እንዳይቀሩ አስቢ! እሱ እግዚአብሔር ብርታቱን ይስጥሽ እንጂ ምን ይደረጋል?! አይ መከራ ሁለት ጨቅላ ልጆቹን አስታቅፏት ጉድ አደርጓት ሄደ
እኮ!...” የሰው ወሬ... ገዳይ ማን እንደሆነ የታወቀው ገበየሁ በሞተ ዕለት ነበር፡፡ ከብቶቹን ፊት ከፊት እያሯሯጠ ሲገሰግስ ሰዎች ተመልክተውት ነበር፡፡ሚስጢሩ
አልተከሰተላቸውም እንጂ፣ ገበየሁን ገድሎ ከብቶቹን ዘርፎ መሄዱን አላወቁም እንጂ አይተውታል።
· “አታውቁትም እንዴ? ጎንቻ የሚባለው ነው እኮ! ኽረ በደንብ እናውቀዋላን! ጥቁር ረዥም? አዎን! ከኢተያ ከተማ አንድም ቀን ጠፍቶ የማያውቅ? ኸረ ሌባ ነው እየተባለ ሲታማ ሰምቻለሁ! ጎንቻ ሌባው ነው እንዴ?! አዎን ጥቁሩ አውቀዋለሁ! ምነው ከወይዘሮ ባንቺይደሩ ቤት የማይጠፋው የሃጂ ቦሩ ልጅ አይደለም እንዴ?! ኸረ ከባለቤቱም ጋር ይታማል ጉድ ነው! ጉድ! አቤት! አቤት!” ውስጥ ውስጡን ሰው ያወራ ጀመር፡፡ ቀስ
በቀስ ደግሞ ጎንቻ ዓለሚቱን የወሸማት መሆኑ ሹክሹክታው ማምለጥ
ጀመረ።
ስልስቱም አርባውም እንደ ቀልድ አለፈ፡፡ ከዓለሚቱ ጭንቅላት ውስጥ የገበየሁ ምስልና ትዝታ ሙሉ ለሙሉ ጠፋ። ትዝታውና ስሙ ያልጠፊው አባባ የታለ? እያሉ ዘወትር ከሚጠይቁት ከእነኝያ በአእምሮም ሆነ በአካል ካልበሰሉ ጨቅላ ህፃናት ጣፋጭ አንደበት ብቻ ነበር።በለቅሶው ዕለት አባታቸው ለዘለዓለም በተለያቸው በዚያን ቀን የነበረው ትርምስና ግርግር ለነሱ ሰርግና ምላሽ ነበር፡፡ ምናልባት የእናታቸው ለቅሶ ቢያስደነግጣቸው እንጂ ከዚያ በኋላ ያለአባት የሚቀሩ የሙት ልጅነታቸው
አልታወቃቸውም ነበር፡፡ ለዚያውም ወንዱ ምትኬ ይሻላል። እሱ ትንሽ ትንሽ በደመነፍሱ ሳይታወቀው አልቀረም፡፡ “እማምዬ አባዬ የታለ አይመታም?”ብሎ ሳይጠይቅ የዋለና ያደረበት ቀን አልነበረም፡፡ ከሁሉ የበለጠ
የምታሳዝነው ደግሞ ትንሿ ሴት ልጁ ነበረች። የዛሬን አይጥራትና በስሟ
ሳይሆን “እናቴ፣ እናቴነሽ” እያለ እያቆላመጠ ነበር የሚጠራት። እሷም
እንደ ወንድሟ አባቷ እየናፈቃት ስለመጣ ታላቅ ወንድሟ የአባቱን ስም እያነሳ ሲጠይቅ የሷም ጥያቄ በመሆኑ ዐይኖቿን በእናቷ ዐይኖች ላይ ታቁለጨልጭ ነበር።
ሁለቱ ህፃናት አባታቸውን ከእናታቸው ዐይኖች ውስጥ እንደሚያገኙት
ሁሉ ዘወትር ዐይን ዐይኖቿን በልምምጥ እያስተዋሉ መወትወታቸውን አላቋረጡም ነበር። የምትመልሳቸው
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ከወደ ጋራው አካባቢ እሪታና ዋይታ ተሰማ፡፡ “ኡ! ኡ!.ኡ.!! የሀገር ያለህ! የመንግሥት ያለህ! የወገን ያለህ! ኡ.ኡ.ኡ. እሪ!” የሚሉ ሰዎች ቁጥራቸው እየተበራከተ ሄደና የህብረት ጩኸታቸውን ያቀልጡት ጀመር፡፡
የመንደሪቱ ነዋሪዎች ዱላ የያዘ ዱላውን ጠመንጃ ያለው ጠመንጃውን እያነሳ የተጣደፈው ባዶ እጁን ለእርዳታ ወደ ዋይታና እሪታው ቦታ ገስገስ በተፈጠረው ድርጊት በመደናገጥ የበለጠ የሰው ሀይል ለማስባሰብ ተኩስ ተተኮስ፡፡
“ቷ! ቷ! . ዷ! ዷ! ህፃናትና ሴቶች ሲቀሩ ሌላው ግልብጥ ብሎ ወጥቶ አካባቢውን አጣበበው። ድርጊቱ እጅግ የሚያስደነግጥ ፍፁም ዐይን ሊያምነው የማይችል ጆሮ ቢሰማው የሚሰቀጥጥ ሆነ፡፡ የዚህ አይነቱ ወንጀል ለብዙ ሰዎች አዲስ ከመሆኑም ሌላ ወንጀሉ የተፈፀመበት ሰው ገበየሁ መሆኑ ደግሞ ህዝቡን እርስ በርሱ አባለው። አንጫጫው። ቀድሞ እዚያ የደረስው ጭንቅላቱን ይዞ “
እግዚኦ! እግዚኦ! ያንተ ያለህ!” እያለ አንዱ
በሌላው ላይ እየዘለለ ያየው ነገር አስደንግጦት ድርጊቱ አስበርግጎት
ቁጣው ከስማይ እንደወረደ ሁሉ ወደ ስማይ ያንጋጥጣል፡፡ መልካም ባህሪ የነበረው ትህትናው ለአንድ ቀን እንኳን ተጓድሎ የማያውቀው ስሙ በክፉ ተነስቶ የማያውቀው ገበየሁ፣ ለትዳሩ ቀና ደፋ የሚለው ገበየሁ፣ ትዳሩ ለሌሎች ምሳሌነት የሚበቃው ገበየሁ የዚህ አይነቱ አስቃቂ ዕጣ ፈንታ ደርሶበት በጫካ ውስጥ ተደፍቶ ይቀራል ብሎ ማመን እጅግ አስቸጋሪ ሆነባቸው፡፡ መሞቱን የሚጠራጠሩ በፍፁም እሱ ሊሆን አይችልም በማለት የሚከራከሩም አልጠፉም ነበር፡፡ ወዲያና ወዲህ ተሯሩጠው ከብቶቹ መዘረፋቸውን ሲያረጋግጡ ግን ከብቶቹን ለመዝረፍ
በመጣ ወንበዴ እጅ የተገደለ እሱ ራሱ ገበየሁ መሆኑን ሳይወዱ በግድ
እያመኑ መጡ፡፡
“እባካችሁ ጎበዝ! እባካችሁ እስቲ ቶሎ ቶሎ ብላችሁ ቅደሙ! ትኩስ ደም ላይ ከደረሰች ልክፍት ነው የሚገድላት! ድንጋጤው ሰው አያደርጋትም!
እባካችሁ ወደ ቤት እሩጡ! ጉዷን ያላወቀች ወደዚሁ እየመጣች ይሆናል
ዋ! እቴን! እሪታው የቤቷ ጉድ መሆኑን ሳታውቅ ድንገት ደሙ ላይ እንዳትቆምና እንዳትጎዳ ፍጠኑ!” አለ አንዱ የቅርብ ጎረቤት ዓላሚቱ እሪታውን ሰምታ እንዳትመጣ እየሰጋ፡፡
“ጎበዝ! ምናልባት ተጠራጥራ ካስቸገረቻችሁ በጉልበትም ቢሆን ይዛችሁ አቆዩአት። ከሞት ታድነው ደሙ ላይ ደርሳ እንዳትለከፍ! አጉል ራሷን
አደጋ ላይ እንዳትጥል ተጠንቀቁ!” ሲሉ ሌላው ጎረቤት አክለው አሳሰቡ፡፡
በዚሁ መሰረት ደህና ደህና ጡንቻ ያላቸው ስድስት ጎረምሶች ወደ ገበየሁ መኖሪያ ቤት ሮጡ፡፡ ዓለሚቱ ምን እንደተፈጠረ ምን በመፈጠር ላይ እንዳለ ቀድማ አውቃዋለች።ባሏ ከብቶቹን ለግጦሽ ካሰማራበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን ሁኔታ ጠንቅቃ ታውቃለች። ጎንቻ እንደፎከረ ያደረገው መሆኑን የተረዳችው ገበየሁ ከብቶቹ እንዲታለቡ ወደ ቤት ይዟቸው
የሚመለስበት ሰዓት ሲያልፍ ነበር፡፡
የተፈፀመውን ድርጊት ፍፁም እንዳላወቀች ሆና ተጨንቃ ሰው ካላስጨነቀች በስተቀር ሀሜትና አሉባልታው እንደማያስቀምጣት ስለምታውቅ ተዘጋጀች።
ተከታትለው የደረሱትን ወንዶች በጭንቀት መልክ እያስተዋለች... እንዴ! ምነው?! ምንድነው? እንዴ! ምን ተፈጠረ?! ገበየሁ ደህና አይደለም እንዴ!? ወየው ጉዴ! ኸረ ባካችሁ ንገሩኝ?! ምንድነው ግርግሩ?!
ጨኸት…የምን ጩኸት ነው? ወየው! ኸረ ዘንድሮ! እኔ እኮ ሲዘገይብኝ ነው ልቤ የነገረኝ ኸረ! ኡኡ ኡ በዚህ ጊዜ ወንዶቹ የምታብድና ራሷን የምትገድል ስለመሰላቸው ደንግጠው ከግራና ቀኝ ሁለቱንም እጆችዋን አፈፍ ፣አፈፍ አድርገው ያዟት። በዚህ ጊዜ ለየላት። እንባዋ ግድቡን እንደ ጣሰ ጎርፍ መንታ መንታ ሆኖ እየተንዶለዶላ በጥፍሯም በንክሻም የተሰበሰበውን ሰው ሁሉ ትፈጀው ጀመር። ጠቅላላ ቤቱን ቀበሮ የገባበት የበግ መንጋ አስመሰለችው። አተራመሰችው። በዚህ ቅፅበት ወዳጅ ጎረቤቱ መጀመሪያ ቤቷን ከዚያም ቀስ በቀስ ደጁን እየሞላው መጣ፡፡
የቅርብ ዘመድ የሆነው ኡኡታውን እዬዬና ዋይታውን ከርቀት እያስማ መጉረፍ ጀመረ። “ዓለሚቱ ጉድ ሆን! ዓላምዬ እጃችን ተቆረጠ! ዓለምዬ ጉድ ፈላ! ውሽታሙ ገበየሁ! አታላዩ ገበየሁ! ልጆችህን ሳትሰናበት ገበየሁ! እሪ” እያለ ከአንጀቱ አለቀሰ፡፡ ዓለሚቱም ለያዥ ለገናዥ እስከምታስቸግር ድረስ እየጮኽች ደረቷን ደለቀች፡፡ያንን አስደናቂ የማስመሰል ችሎታዋን የታዘበ ሰው የዓለሚቱን እንከን የለሽ መሪ የፊልም ተዋናይነት ያለ አንዳች ጥርጥር ይመሰክርላታል፡፡ ያንን የተዋጣለት ድራማ ሰርታ ካጠናቀቀችና የሚስኪኑ ገበየሁ አሟሟት ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጎ አስከሬኑ አሰላ ከተማ ሆስፒታል ተወስዶ ከተመረመረ በኋላ በተወለደ በሰላሳ
ሶስተኛ ዓመት ዕድሜው ወደ ዘለዓለማዊ ቤቱ ወደ መቃብር ወረደ።
“ቤቴን ትዳሬን ልጆቼን ሚስቴን” እንዳለ ሳያስበው እንደወጣ ቀረ። መሪር ሀዘንና የማይጠፋ ፀፀትን በወላጆቹና በወዳጅ ዘመዶቹ ልብ ውስጥ ጥሎ አለፈ... ዓለሚቱ ሀዘኑ ያደከማት፣ የደቆሳት መሰለች።
“ከእንግዲህ ጠንከር በይ እንጂ ዓለሚቱ? ከዚህ በላይ ራስሽን መጉዳት የለብሽም፡፡ ራስሽን ከዚህ በላይ ጎድተሽ እነዚህ ልጆች ሜዳ ላይ እንዳይቀሩ አስቢ! እሱ እግዚአብሔር ብርታቱን ይስጥሽ እንጂ ምን ይደረጋል?! አይ መከራ ሁለት ጨቅላ ልጆቹን አስታቅፏት ጉድ አደርጓት ሄደ
እኮ!...” የሰው ወሬ... ገዳይ ማን እንደሆነ የታወቀው ገበየሁ በሞተ ዕለት ነበር፡፡ ከብቶቹን ፊት ከፊት እያሯሯጠ ሲገሰግስ ሰዎች ተመልክተውት ነበር፡፡ሚስጢሩ
አልተከሰተላቸውም እንጂ፣ ገበየሁን ገድሎ ከብቶቹን ዘርፎ መሄዱን አላወቁም እንጂ አይተውታል።
· “አታውቁትም እንዴ? ጎንቻ የሚባለው ነው እኮ! ኽረ በደንብ እናውቀዋላን! ጥቁር ረዥም? አዎን! ከኢተያ ከተማ አንድም ቀን ጠፍቶ የማያውቅ? ኸረ ሌባ ነው እየተባለ ሲታማ ሰምቻለሁ! ጎንቻ ሌባው ነው እንዴ?! አዎን ጥቁሩ አውቀዋለሁ! ምነው ከወይዘሮ ባንቺይደሩ ቤት የማይጠፋው የሃጂ ቦሩ ልጅ አይደለም እንዴ?! ኸረ ከባለቤቱም ጋር ይታማል ጉድ ነው! ጉድ! አቤት! አቤት!” ውስጥ ውስጡን ሰው ያወራ ጀመር፡፡ ቀስ
በቀስ ደግሞ ጎንቻ ዓለሚቱን የወሸማት መሆኑ ሹክሹክታው ማምለጥ
ጀመረ።
ስልስቱም አርባውም እንደ ቀልድ አለፈ፡፡ ከዓለሚቱ ጭንቅላት ውስጥ የገበየሁ ምስልና ትዝታ ሙሉ ለሙሉ ጠፋ። ትዝታውና ስሙ ያልጠፊው አባባ የታለ? እያሉ ዘወትር ከሚጠይቁት ከእነኝያ በአእምሮም ሆነ በአካል ካልበሰሉ ጨቅላ ህፃናት ጣፋጭ አንደበት ብቻ ነበር።በለቅሶው ዕለት አባታቸው ለዘለዓለም በተለያቸው በዚያን ቀን የነበረው ትርምስና ግርግር ለነሱ ሰርግና ምላሽ ነበር፡፡ ምናልባት የእናታቸው ለቅሶ ቢያስደነግጣቸው እንጂ ከዚያ በኋላ ያለአባት የሚቀሩ የሙት ልጅነታቸው
አልታወቃቸውም ነበር፡፡ ለዚያውም ወንዱ ምትኬ ይሻላል። እሱ ትንሽ ትንሽ በደመነፍሱ ሳይታወቀው አልቀረም፡፡ “እማምዬ አባዬ የታለ አይመታም?”ብሎ ሳይጠይቅ የዋለና ያደረበት ቀን አልነበረም፡፡ ከሁሉ የበለጠ
የምታሳዝነው ደግሞ ትንሿ ሴት ልጁ ነበረች። የዛሬን አይጥራትና በስሟ
ሳይሆን “እናቴ፣ እናቴነሽ” እያለ እያቆላመጠ ነበር የሚጠራት። እሷም
እንደ ወንድሟ አባቷ እየናፈቃት ስለመጣ ታላቅ ወንድሟ የአባቱን ስም እያነሳ ሲጠይቅ የሷም ጥያቄ በመሆኑ ዐይኖቿን በእናቷ ዐይኖች ላይ ታቁለጨልጭ ነበር።
ሁለቱ ህፃናት አባታቸውን ከእናታቸው ዐይኖች ውስጥ እንደሚያገኙት
ሁሉ ዘወትር ዐይን ዐይኖቿን በልምምጥ እያስተዋሉ መወትወታቸውን አላቋረጡም ነበር። የምትመልሳቸው
👍1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጋሻዬነህ ጌታነህ ይባላል» ብላ ጸጥ አለች። ከወዲህም ከወዲያም ከጣራውም ከወለሉም ላይ ድምፅ ስደት ገባ።
ከማን የተወለደ? የመቼው? የት የነበረ? ብላ የተሰደደውን ድምፅ መለሰችው:: ነገሩ በመፋፋሙና ጥያቄው በመድራቱ የመጣው ይምጣ ብዩ ዐይኔን ጨፍኜ ገባሁ፡፡
ምንም ሳልናር ተቀመጥኩ፡፡ ጋሻይነህ እናቴ እግሮች መካከል ቆሟል።
የውብነሽ ከእናቴ ፊት ለፊት ቆማ የአቤቱታ መልስ የሚጠባበቅ ድኃ መስላለች።እናቴ ዘወር ብላ ካየችኝ በኋላ ለዛ ባጣ ፈገግታ ገረመመችኝ፡፡ «የጌታነህማ ልጅ ከሆነ እሱው ራሱ ይናገር፣ ይኸው መጣ! አንቺ ምን ታጎበጉቢያለሽ» አለችና ዐይኖቿን ወደ ጋሻዬነህ መለሰቻቸው:: አቀረቀርኩ፡፡ ከንፈሮቼ ተጣበቁ፡፡
ያመጣኸውን ብታመጣ በደስታ እቀበልልሃለሁ፣ እፈጽምልሃለሁ ብለሽ
የአቦን ስም ጠርተሽ ምለሻል:: አሁን ወዲያ ወዲህ እንዳትይ! በዚህ ወጥቶ በዚያ ወርዶ ብሎ ነገር የለም፡፡ ታሪኩንና ሁኔታን ሁሉ ቀስ በቀስ ነገና ከነገ ወዲያ
እንዘረዝርልሻለን፡፡ አሁን ግን ምንም ምንም ሳትይ ይህን የአተር ክክ የመሰለ ልጅ ደስ ብሎሽ ተቀበይን፡፡ የሚያኮራና የሚያስደስት ነው:: ከዛሬ ስድስት ዓመት
በፊት የተወለደ የጌታነህ ልጅ ነው» ብላ በሙሉ ልብ ተዝናንታ ተቀመጠች፡፡
ከተሽከምኩት የሐሳብ ቀንበር ላይ ትንሽ ተጎርዶ ወደቀ፡፡ ደቂቃዎች ተውዘገዘጉ፡፡
እናቴ በሐሳብ ላይ እንዳለች ጋሻዬነህ ከእግሮቿ መኻል ሹልክ ብሎ ወጣና ትከሻዬን ይዞ ከጐኔ ቆመ:: ጉልህ መልስና ድንቅ ምስክርነት ነበር፡፡
እናቴ ወደ ጎን ዘወር ብላ ስታይ ሰርቀው ከሚመለከቷት ዐይኖቼ ጋር ተጋጨች፡፡ የእኔዎቹ ተሰበሩ፡፡ ፍርሃት ሳይሆን ትሕትና ሰበራቸው።
«ይሁና! አበጀህ! ደግ አረክ! ታዲያ ምን ኣለበት እንኳን ወንድ ልጅና፣ሴትም ልጅ ወልዳ ትመጣለች ! ቀና በል! የምን ማቀርቀር ነው:: ያንበሳ ግልገል
የመሰለ ልጅ ነው ያመጣኸው! እኔ እናትህ ባልምል ባልገዘትስ አንተን ልጄን
አሳፍርሃለሁ እንዴ? ደስ የሚል እንጂ የሚያሳፍር አይደለም፡፡ ያኔዬስ ቢሆን
መላውን አጥቼውና የሴት ነገር ሆኖ ተበሳጭቼ ነው እንጂ የኋላ ኋላ ሳልጠጣትና ሳያንገበግበኝ ቀርቶ መሰለህ: ሽንፍላችን ስስ ነው:: አንችልም! አንኳን አንድ ሁለትና ሦስት ቢሆንሳ? እስከ ዛሬ ድረስ ደብቀሽኝ በመኖርሀ ግን ቀስ ብለን እንወቃቀስበታለን» ብላ ጋሻዬነህን ወስዳ አገላብጣ ሳመችው። የደስታና የርኅራኄ እንባ ዐይኖቿ ላይ ተንቀዋለለ።
ጨምደድ ባለው ፊቷ ላይ የኃፍረትና የጸጸት ስስ ፈገግታ ታየ። አምጣ አምጣ እንደ ተገላገለች ነፍሰ ጡር እኔም የሐሳቤን እትብት አስቆርጡ አፎይ
አልኩ፡፡
«አቤት እኔ! ይኸስ እውነትም እልል በይ የሚያሰኝ ነው፡፡ በል አንተ ትልቁ ልጅ
ደግሞ ሳመኝ፡፡ ምንስ ቢሆን ከጥጃይቱ በፊት እናቲቱ” ይሉ የለ፡፡ ከዚህ የበለጠ
ዓለም የት ይገኛል» ብላ ከመናገሯ እመር ብዬ ሄጀ ተሳሳምን፡፡ የውብነሽ በደስታ
ተፍነከነከች፡፡ ደሜ የፈንጠዚያ ግልቢያ ጋለበ። ዐይኖቼ በእናቴ በኩል የሚደረገውን የተስፋና የጉጉት ውጤት አፍጥጠው ተመለከቱ። በእናቴ የፍቅር
ሚዛን ላይ የዱሮው ጌታነህ ለመሆን ተቃረብኩ፡፡ ወንዙን ላደነቀ ምንጩን
ማሳየት አስፈላጊ በመሆኑ የጋሻዬነህን ምንጭ ማሳየት አስፈላጊ ነው፡፡
ተመስገን! ተመስገን! ክብርህ ይስፋ! እንኳን ለዚህ ያበቃኸኝ! ኖረህ ኖረህ ይህን የመሰለ ልጅ ይዘህልኝ ስትመጣ ምን ከፍቶኝ! አቦዬም ስለታቸውን አገኙ፡፡ ትንሽም ቅር የሚለኝ እንደ ወንድሞችህና እኅቶችህ ወግ ማረግ...አረ ምን አባቱ! ይሁን! ዞሮ ዞሮ ለዚሁ አይደል?» አለችና ከሕሊናዋ ጋር ለመግባባት አስተያየቷን መለወጥ ሞከረች፡፡ እንደ ወንድሞቼና እህቶቼ እንድሆንላት ስትመኝ የነበረው ምኞቷና ፍላጎቷ ሁሉ በዚህ ባልጠበቀችው ሁኔታና ኢጋጣሚ ከሰመ፡፡
«ደስ አለሽ? እኛማ በጣም ፈርተንና ተጨንቀን ነበር፡፡ እንዲህ በቀላሉ
ይቀናናል፣ እንዲህ ባለ ሁኔታ ይሳካልናል ብለን በፍፁም አላሰብንም ነበር?» ብላ
የእናቴን ኃይለኛነትና ትፈሪነት ለማስገንዘብ ሞከረች፡፡ እግረ መንገዷንም የእናቴ ስሜት ወደ እኛ እንዲያዘነብል ማጎሳመሷ ነበር፡፡
«እስኪ ተይኝ ልጀ! የዛሬዋን ደስታዩን ዝግ ብለን ልባችንን አስፍተን እንጫወታለን፡፡ ጌታነህ እንበሳ ከነነፍሱ ይዞልኝ መጥቷል» ካለች በኋላ ጋሻዬነህን
ለየውብነሽ ሰጥታ ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ሄደች። እኔና የውብነሽ በደስታ
ተቃቅፈን ተሳሳምን። ጋሻዬነህንም ለሁለት ኣንሥተን «አንተ ዕድለኛ» ብለን
በየአቅጣጫችን ያለውን ጉንጩን ስመን ወደየነበርንበት ቦታ ተመልሰን
ተቀመጥን። ሰው በደስታ ይፈነዳ ሲሆን ያለጥርጥር እፈነዳ ነበር። አንዲት
ሠራተኛ የእጅ ውሃ አምጥታ እንዳስታጠበችን እናታችን ገባች። ይኽነዩ ነበር የቀድሞው የየወዲያነሽ ሕይወት ትዝ ያለኝና መንፈሴ ስለ ባለቤቴ
የተሠቃየው:: በሌሎች ሁለት ሠራተኞች ደግሞ ምግብና መጠጥ በየተራ ቀረበ።
«የቤታችንን የሲሳይ ርጥበት አሳምሬ ስለማውቀው በቀረበው መስተንግዶ
አልተደነቅሁም፡፡
እህል ብቻ ሳይሆን የደስታ እንክብክብ ጎረስኩ፡፡ ባልገመትኩት አኳኋን ወኔና ብርታት አካበትኩ፡፡ አዲስ የኑሮ ተስፋ ከፊት ለፊቴ ተዘረጋ፡፡ አጋጣሚና
ድል የሚባለው ይኸ ይሆን? እስከ ማለት ደረስኩ፡፡ እናቴ ወደ እፏ ከላከችው
ይልቅ ለእኔና ለጋሻዬነህ ያጎረሰችን ይበልጣል። የጣቶቿ ጫፎች ከንፈሮቼን
እየነኩ ሲመለሱ የእናትነቷን ውድ ፍቅር እያቀበሉኝ ተመለሱ።
ጋሻዬነህ አካባቢውን ስለተለማመደው ያ በግርታ መጦ የነበረው ፊቱ እጥፍ ፈገግታ አንዠረገገ። ገበታው ከፍ ኣለ። የአዲሱ ግንኙነት ማዕድ ግን በሰፊው ቀጠለ። እናቴ ብርጭቆዋ ውስጥ የነበረችውን ጠላዋን ተጎንጭታ
ጉሮሮዋን ካራሰች በኋላ እናንተ ግን ምስጥ ናችሁ፣ ልባችሁ አይገኝም፡፡
የገረመኝ ደግሞ ሆን ብላችሁ አባታችሁ በሌለበት ቀን መምጣታችሁ ነው::
የናንተን ብልጠት ማን ያገኘዋል» አለችና ተንኮል የሌለበት ሣቅ ሣቀች፡፡
«ከአባታችን ይልቅ አንቺን በመጀመሪያ ብንጠይቅና ብናሸንፍ፣ አንቺ
ካየሽው በኋላ የምትይንን ለማወቅ ብለን ነው:: በተለይ የዛሬዋን ቀን ጠብቀን
የመጣነው» ብላ የውብነሽ በጠላዋ ውስጥ የምትታየውን የገዛ ፊቷን ምስል
ለማየት አንገቷን ወደ ብርጭቆው አሰገገችው።
«ኧረ ለመሆኑ አንቺ ይኸ ልጅ መወለዱን የሰማሽውና ያወቅሽው መቼ ነው?» ብላ መገረሟን በሚገልጽ ስሜት ጠየቀቻት። የውብነሽ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ «አጅሬ መች እንዲህ የዋዛ ሰው ነውና! እኔም ያየሁት አሁን በቅርቡ ነው:: ያም ሆነ ይህ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ የቀረውን ተይኝ» በማለት ወቀሳ የቦረቦረው ድጋፍ አደረገችልኝ። የጋሻዬነህ እናት ማንነት እና ስሟ ተጠቅሶ ባለመነገሩ በውስጤ የሚፈራገጠውን ጭንቀቴን አጠቃልዬ አልገደልኩም፡፡
«ኧረ ለመሆኑ እናቱ ማን ትባላለች? የማን ልጅ ትሆን? አልነገራችሁኝም እኮ?» ብላ ሁለታችንንም. በየተራ አየችን፡፡ እኔና የውብነሽ ተፋጠጥን! ይህን ለጊዜው በምሥራችነት የማይነገር ታላቅ ጉዳይ ማን ያርዳ?
የውብነሽ መልስ ለመስጠት አልዘገየችም፡፡ «የእናቱ ጉዳይ ግልጽም
??ስውርም ነው:: ከዚህ ቤት ይጀምርና ወደ ሌላ ሰፊ ሥፍራ ይጓዛል። ዳቦውን
ገምጦ ምጣዱን መጥላት አይገባም፡፡ የዚህ ልጅ እናት አንቺ እንደምትመኘው
የማንም ትልቅ ሰው ልጅ አይደለችም፡፡ በደፈናው የሰው ልጅ ነች፡፡ እስከ አሁን
ድረስ ፈርተናል ፣ተጨንቀናል፣ ከእንግዲህ ግን በቃ! የዚህ ልጅ እናት የመከራ
እሳት የለበለባት፡ የሥቃይ ቀንበር የተጫናት፣ የሰው ፊት እንደ እሳት ነበልባል
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ጋሻዬነህ ጌታነህ ይባላል» ብላ ጸጥ አለች። ከወዲህም ከወዲያም ከጣራውም ከወለሉም ላይ ድምፅ ስደት ገባ።
ከማን የተወለደ? የመቼው? የት የነበረ? ብላ የተሰደደውን ድምፅ መለሰችው:: ነገሩ በመፋፋሙና ጥያቄው በመድራቱ የመጣው ይምጣ ብዩ ዐይኔን ጨፍኜ ገባሁ፡፡
ምንም ሳልናር ተቀመጥኩ፡፡ ጋሻይነህ እናቴ እግሮች መካከል ቆሟል።
የውብነሽ ከእናቴ ፊት ለፊት ቆማ የአቤቱታ መልስ የሚጠባበቅ ድኃ መስላለች።እናቴ ዘወር ብላ ካየችኝ በኋላ ለዛ ባጣ ፈገግታ ገረመመችኝ፡፡ «የጌታነህማ ልጅ ከሆነ እሱው ራሱ ይናገር፣ ይኸው መጣ! አንቺ ምን ታጎበጉቢያለሽ» አለችና ዐይኖቿን ወደ ጋሻዬነህ መለሰቻቸው:: አቀረቀርኩ፡፡ ከንፈሮቼ ተጣበቁ፡፡
ያመጣኸውን ብታመጣ በደስታ እቀበልልሃለሁ፣ እፈጽምልሃለሁ ብለሽ
የአቦን ስም ጠርተሽ ምለሻል:: አሁን ወዲያ ወዲህ እንዳትይ! በዚህ ወጥቶ በዚያ ወርዶ ብሎ ነገር የለም፡፡ ታሪኩንና ሁኔታን ሁሉ ቀስ በቀስ ነገና ከነገ ወዲያ
እንዘረዝርልሻለን፡፡ አሁን ግን ምንም ምንም ሳትይ ይህን የአተር ክክ የመሰለ ልጅ ደስ ብሎሽ ተቀበይን፡፡ የሚያኮራና የሚያስደስት ነው:: ከዛሬ ስድስት ዓመት
በፊት የተወለደ የጌታነህ ልጅ ነው» ብላ በሙሉ ልብ ተዝናንታ ተቀመጠች፡፡
ከተሽከምኩት የሐሳብ ቀንበር ላይ ትንሽ ተጎርዶ ወደቀ፡፡ ደቂቃዎች ተውዘገዘጉ፡፡
እናቴ በሐሳብ ላይ እንዳለች ጋሻዬነህ ከእግሮቿ መኻል ሹልክ ብሎ ወጣና ትከሻዬን ይዞ ከጐኔ ቆመ:: ጉልህ መልስና ድንቅ ምስክርነት ነበር፡፡
እናቴ ወደ ጎን ዘወር ብላ ስታይ ሰርቀው ከሚመለከቷት ዐይኖቼ ጋር ተጋጨች፡፡ የእኔዎቹ ተሰበሩ፡፡ ፍርሃት ሳይሆን ትሕትና ሰበራቸው።
«ይሁና! አበጀህ! ደግ አረክ! ታዲያ ምን ኣለበት እንኳን ወንድ ልጅና፣ሴትም ልጅ ወልዳ ትመጣለች ! ቀና በል! የምን ማቀርቀር ነው:: ያንበሳ ግልገል
የመሰለ ልጅ ነው ያመጣኸው! እኔ እናትህ ባልምል ባልገዘትስ አንተን ልጄን
አሳፍርሃለሁ እንዴ? ደስ የሚል እንጂ የሚያሳፍር አይደለም፡፡ ያኔዬስ ቢሆን
መላውን አጥቼውና የሴት ነገር ሆኖ ተበሳጭቼ ነው እንጂ የኋላ ኋላ ሳልጠጣትና ሳያንገበግበኝ ቀርቶ መሰለህ: ሽንፍላችን ስስ ነው:: አንችልም! አንኳን አንድ ሁለትና ሦስት ቢሆንሳ? እስከ ዛሬ ድረስ ደብቀሽኝ በመኖርሀ ግን ቀስ ብለን እንወቃቀስበታለን» ብላ ጋሻዬነህን ወስዳ አገላብጣ ሳመችው። የደስታና የርኅራኄ እንባ ዐይኖቿ ላይ ተንቀዋለለ።
ጨምደድ ባለው ፊቷ ላይ የኃፍረትና የጸጸት ስስ ፈገግታ ታየ። አምጣ አምጣ እንደ ተገላገለች ነፍሰ ጡር እኔም የሐሳቤን እትብት አስቆርጡ አፎይ
አልኩ፡፡
«አቤት እኔ! ይኸስ እውነትም እልል በይ የሚያሰኝ ነው፡፡ በል አንተ ትልቁ ልጅ
ደግሞ ሳመኝ፡፡ ምንስ ቢሆን ከጥጃይቱ በፊት እናቲቱ” ይሉ የለ፡፡ ከዚህ የበለጠ
ዓለም የት ይገኛል» ብላ ከመናገሯ እመር ብዬ ሄጀ ተሳሳምን፡፡ የውብነሽ በደስታ
ተፍነከነከች፡፡ ደሜ የፈንጠዚያ ግልቢያ ጋለበ። ዐይኖቼ በእናቴ በኩል የሚደረገውን የተስፋና የጉጉት ውጤት አፍጥጠው ተመለከቱ። በእናቴ የፍቅር
ሚዛን ላይ የዱሮው ጌታነህ ለመሆን ተቃረብኩ፡፡ ወንዙን ላደነቀ ምንጩን
ማሳየት አስፈላጊ በመሆኑ የጋሻዬነህን ምንጭ ማሳየት አስፈላጊ ነው፡፡
ተመስገን! ተመስገን! ክብርህ ይስፋ! እንኳን ለዚህ ያበቃኸኝ! ኖረህ ኖረህ ይህን የመሰለ ልጅ ይዘህልኝ ስትመጣ ምን ከፍቶኝ! አቦዬም ስለታቸውን አገኙ፡፡ ትንሽም ቅር የሚለኝ እንደ ወንድሞችህና እኅቶችህ ወግ ማረግ...አረ ምን አባቱ! ይሁን! ዞሮ ዞሮ ለዚሁ አይደል?» አለችና ከሕሊናዋ ጋር ለመግባባት አስተያየቷን መለወጥ ሞከረች፡፡ እንደ ወንድሞቼና እህቶቼ እንድሆንላት ስትመኝ የነበረው ምኞቷና ፍላጎቷ ሁሉ በዚህ ባልጠበቀችው ሁኔታና ኢጋጣሚ ከሰመ፡፡
«ደስ አለሽ? እኛማ በጣም ፈርተንና ተጨንቀን ነበር፡፡ እንዲህ በቀላሉ
ይቀናናል፣ እንዲህ ባለ ሁኔታ ይሳካልናል ብለን በፍፁም አላሰብንም ነበር?» ብላ
የእናቴን ኃይለኛነትና ትፈሪነት ለማስገንዘብ ሞከረች፡፡ እግረ መንገዷንም የእናቴ ስሜት ወደ እኛ እንዲያዘነብል ማጎሳመሷ ነበር፡፡
«እስኪ ተይኝ ልጀ! የዛሬዋን ደስታዩን ዝግ ብለን ልባችንን አስፍተን እንጫወታለን፡፡ ጌታነህ እንበሳ ከነነፍሱ ይዞልኝ መጥቷል» ካለች በኋላ ጋሻዬነህን
ለየውብነሽ ሰጥታ ወደ እንግዳ መቀበያ ክፍል ሄደች። እኔና የውብነሽ በደስታ
ተቃቅፈን ተሳሳምን። ጋሻዬነህንም ለሁለት ኣንሥተን «አንተ ዕድለኛ» ብለን
በየአቅጣጫችን ያለውን ጉንጩን ስመን ወደየነበርንበት ቦታ ተመልሰን
ተቀመጥን። ሰው በደስታ ይፈነዳ ሲሆን ያለጥርጥር እፈነዳ ነበር። አንዲት
ሠራተኛ የእጅ ውሃ አምጥታ እንዳስታጠበችን እናታችን ገባች። ይኽነዩ ነበር የቀድሞው የየወዲያነሽ ሕይወት ትዝ ያለኝና መንፈሴ ስለ ባለቤቴ
የተሠቃየው:: በሌሎች ሁለት ሠራተኞች ደግሞ ምግብና መጠጥ በየተራ ቀረበ።
«የቤታችንን የሲሳይ ርጥበት አሳምሬ ስለማውቀው በቀረበው መስተንግዶ
አልተደነቅሁም፡፡
እህል ብቻ ሳይሆን የደስታ እንክብክብ ጎረስኩ፡፡ ባልገመትኩት አኳኋን ወኔና ብርታት አካበትኩ፡፡ አዲስ የኑሮ ተስፋ ከፊት ለፊቴ ተዘረጋ፡፡ አጋጣሚና
ድል የሚባለው ይኸ ይሆን? እስከ ማለት ደረስኩ፡፡ እናቴ ወደ እፏ ከላከችው
ይልቅ ለእኔና ለጋሻዬነህ ያጎረሰችን ይበልጣል። የጣቶቿ ጫፎች ከንፈሮቼን
እየነኩ ሲመለሱ የእናትነቷን ውድ ፍቅር እያቀበሉኝ ተመለሱ።
ጋሻዬነህ አካባቢውን ስለተለማመደው ያ በግርታ መጦ የነበረው ፊቱ እጥፍ ፈገግታ አንዠረገገ። ገበታው ከፍ ኣለ። የአዲሱ ግንኙነት ማዕድ ግን በሰፊው ቀጠለ። እናቴ ብርጭቆዋ ውስጥ የነበረችውን ጠላዋን ተጎንጭታ
ጉሮሮዋን ካራሰች በኋላ እናንተ ግን ምስጥ ናችሁ፣ ልባችሁ አይገኝም፡፡
የገረመኝ ደግሞ ሆን ብላችሁ አባታችሁ በሌለበት ቀን መምጣታችሁ ነው::
የናንተን ብልጠት ማን ያገኘዋል» አለችና ተንኮል የሌለበት ሣቅ ሣቀች፡፡
«ከአባታችን ይልቅ አንቺን በመጀመሪያ ብንጠይቅና ብናሸንፍ፣ አንቺ
ካየሽው በኋላ የምትይንን ለማወቅ ብለን ነው:: በተለይ የዛሬዋን ቀን ጠብቀን
የመጣነው» ብላ የውብነሽ በጠላዋ ውስጥ የምትታየውን የገዛ ፊቷን ምስል
ለማየት አንገቷን ወደ ብርጭቆው አሰገገችው።
«ኧረ ለመሆኑ አንቺ ይኸ ልጅ መወለዱን የሰማሽውና ያወቅሽው መቼ ነው?» ብላ መገረሟን በሚገልጽ ስሜት ጠየቀቻት። የውብነሽ ካቀረቀረችበት ቀና ብላ «አጅሬ መች እንዲህ የዋዛ ሰው ነውና! እኔም ያየሁት አሁን በቅርቡ ነው:: ያም ሆነ ይህ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ የቀረውን ተይኝ» በማለት ወቀሳ የቦረቦረው ድጋፍ አደረገችልኝ። የጋሻዬነህ እናት ማንነት እና ስሟ ተጠቅሶ ባለመነገሩ በውስጤ የሚፈራገጠውን ጭንቀቴን አጠቃልዬ አልገደልኩም፡፡
«ኧረ ለመሆኑ እናቱ ማን ትባላለች? የማን ልጅ ትሆን? አልነገራችሁኝም እኮ?» ብላ ሁለታችንንም. በየተራ አየችን፡፡ እኔና የውብነሽ ተፋጠጥን! ይህን ለጊዜው በምሥራችነት የማይነገር ታላቅ ጉዳይ ማን ያርዳ?
የውብነሽ መልስ ለመስጠት አልዘገየችም፡፡ «የእናቱ ጉዳይ ግልጽም
??ስውርም ነው:: ከዚህ ቤት ይጀምርና ወደ ሌላ ሰፊ ሥፍራ ይጓዛል። ዳቦውን
ገምጦ ምጣዱን መጥላት አይገባም፡፡ የዚህ ልጅ እናት አንቺ እንደምትመኘው
የማንም ትልቅ ሰው ልጅ አይደለችም፡፡ በደፈናው የሰው ልጅ ነች፡፡ እስከ አሁን
ድረስ ፈርተናል ፣ተጨንቀናል፣ ከእንግዲህ ግን በቃ! የዚህ ልጅ እናት የመከራ
እሳት የለበለባት፡ የሥቃይ ቀንበር የተጫናት፣ የሰው ፊት እንደ እሳት ነበልባል
👍3👏1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ጋሻዬነህ ከእናቴ ጋር ውሉ አደረ፡፡ የየወዲያነሽ የእናትነት አንጀት በናፍቆት ተላወሰ፡፡ ሮብ ጧት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን «ምነው ዝም አልክ ጌታነህ? ረሳኸው እንዴ? ከጋሼ ጉልላት ጋር ምን ምን ነበር የተባባላችሁት?
ሂድና አምጣው እንጂ» አለችኝ፡፡
“ምናልባት ዛሬ የውብነሽ ታመጣው ይሆናል» አልኩና እንደገና ደግሞ
«ምናለባት ጋሻዬነህን ለእነርሱ ብንሰጣቸውና እኔና አንቺ ደግሞ….ሌላ» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ደረቷን ሁለት ጊዜ በጥፊ ደቃችና «ህ! እንዴት ያለህው ዓለመኛ ነህ! ምነው ምን በወጣኝ! ዕድሜ ላንተ እያልኩ ዐይን ዐይኑን እንዳላይ ነው!» ብላ ከነጥርጣሬዋ ዝም አለች።
ሐሳብን ማሻሻልና ፈጽሞም መለወጥ አንድ ዐይነት ዕድገት በሆኑ የሐሳቧ መለወጥና ተቃውሞዋ ደስ አለኝ፡፡ ለጥያቄዋ መልስ ሳልሰጥ ወደ ሥራ ሄድኩ፡፡
የውብነሽ ቀንም ሆነ ማታ ብቅ ሳትል ቀረች፡፡ የሮብ ጀንበር ጠልቃ የሐሙሷ ተወለደች፡፡ አዲሱ የፍርሃት ሸክም ከየወዲያነሽ ይልቅ እኔን ከበደኝ፡፡ ከማታ
ትምህርት መልስ ሻይ እየጠጣን ስናወራ አንዱን ተረስቶ የቀረ የጋሻዬነህን የሒሳብ ደብተር እያገላበጠች «እሷ መች ሥራ አጣችና ነው ይዛው ትመጣለች
የምትለው? እኔ እኮ ነገሩ የገባኝ የመማሪያ ደብተሩን ይዛ ስትሒድ ነው» ብላ ወደ ራሷ ደብተሮች መለስ አለች፡፡
«እኔን ያሠጋኝ ሌላው አይደለም.....አባባ ይመለሳል ከተባለበት ቀን ቀደም ብሎ ቢመለስና ይኸ ልጅ የማን ነው ልጅ? ብሎ ቢጠየቅ ምን ይላሉ?
እናቴ ገና እንማከራለን ነው ያለችኝ እንጂ ሌላ የተነጋገርነው ነገር የለም ከማለቴ፣ የማን ልጅ እንዲባልልህ ትፈልጋለህ? የጌታነህ ልጅ ነው ብለው
ይነግሩልሃላ» ብላ ኩታ አጣፍቶ የመልበስ ያህል ጉዳዩን አቃልላ መለሰችልኝ።
«እንዴት አንቺ? እኔ እኮ ገና ብዙ ግብግብና ትግል ይጠብቀኛል።
የሙሉ ድሌ ቀኔ ገና ነው:: ምኑ ተያዘና!ምኑ ተነካና! እንዴት አድርጌ እንደምገጥመውና ድል እንደማደርገው ዕቅድና ብልሃቴ አልተጠናቀቀም፡፡ወደፊት የሚቀረኝ የትግል ጉራንጉር ያለፉትን የመከራና የትግል ገድሎች ሁሉ ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ ቀሪው ትግል በዕድልና በአጋጣሚ የማምንበት ነገር
የለም፡፡ የሚጠብቀኝ ውጣ ውረድ ሁሉ በበቂ ምክንያትና በተግባር የሚመራ ነው። «የዘልማድ ዝላይና ባወጣ ያውጣኝ በቃው! በቂ ምክንያት ጥሩ የተግባር
ዋስትና» ብዬ በመጀመር ለወደፊት ከሚያጋጠሙኝ አንደንድ ችግሮች መኻል አንዳንዶቹን በከፊል አዋየኋት፡፡
ዓርብ ከጧቱ ሁለት ሰዓት ላይ የውብነሽ ጋሻዬነህን ይዛ መጣች።
የሚያምር አዲስ ልብስ ለብሶ
ከፈገግታው ጋር ሲታይ የመስከረም ዝናብ ያጠባት
የለጋ ዘንባባ ተክል መስሏል። የወዲያነሽ ግልገሏን አስከትላ ጢሻ ውስጥ እንደምትገባ ሰስ ልጅዋን አስከትላ ወደ ጓዳ ገባች። እኔና የውብነሽ ወጣ ብለን ሰበሰቡ ላይ እንደቆምን «አባባ የነገ ሳምንት ከሰዓት በኋላ ይገባል፡፡ ባለቢትህን እንዴት አድርገን እሱ ፊት እንደምናቀርባት፡ አንተም ምንና ምን እያልክ መናገርና ማስረዳት እንዳለብህ አንድ ባንድ አውጥተን አውርደን ጨርሰናል» ብላ ስለ እኛ ሕይወት እኔና ባለቤቴ ያልተካፈልንበትን የአፈጻጸም ዕቅድ አረዳችኝ፡፡
የችግሬን ዐይነትና ዓላማዬን የማውቀው እኔ ሆኜ ሳለሁ መወከልና ማስፈጸም
የማይገባቸው እኅቴና እናቴ አፈ ቀላጤ ሆነን እንገኝ ሲሉ በመስማቴ ተናደድኩ፡፡
አልተዋጠልኝም፡፡
የአባቴ ግብዝነትና ቁጣዉ፣ ግትርነቱንና የመጣ ይምጣ ባይነቱ፣ እንደ ጨካኝ አገረ ገዢ ፊት ለፊት ቆሞ እንደ እሳት ፈጀኝ፡፡ «ማታ ከትምህርት ቤት
መልስ ከየወዲያነሽ ጋር እንድትመጡ፣ ነገሩን አብራራልሃለሁ። አሁን ግን
ቸኩያለሁ ደኀና ዋል» ብላኝ ቶሉ ብለህ ና እንደ ተባለ መልእክተኛ ጥላኝ ሄደች። አእምሮዬ በሐሳብ ተወቃ፡፡ ሁለመናዬ ብው ብሎ ጋመ፡፡ አዳዲስ ጭንቀቶች በውስጤ ተራወጡ፡፡ የሐሳቤ አድማስ ለመጥበብም ሆነ ለመስፋት ባለመቻሉ መረጋጊያ አጣሁ፡፡
ጎርፍ እንደ ገረሰሰው ዛፍ ግድግዳውን ተደግፌ ቆምኩ፡፡ የወዲያነሽ ከወደ ውስጥ መጥታ «ከምን ጊዜው ሄደች? ያንተ ነገር እኮ...አናደድካት እንዴ?» ብላ
በሥጋት አዘል ሁኔታ ጠየቀችኝ፡፡ «ቸኩላ ነበር፡ ታናድደኛለች እንጂ ምን አናድዳታለሁ፡፡ የማይጠቅሙሽ እጠቅምሻለሁ፣ የሚያጠፉሽ አለማሻለሁ፣
የሚገድሉሽ አድንሻለሁ ሲሉሽ አትናደጂም? አሁን የነገረችኝን ማታ ስትነግረኝ ትሰሚያታለሽ፡፡ አሁን ወደ ሥራሽ ሂጂ» ብያት ዝም አልኩ፡፡ የእርሷ ከአጠገቤ
ገለል ማለት የሚረዳኝ ስለ መሰላት ተመልሳ ገባች፡፡ በአካባቢዬ የሚገኙት ነገሮች
ሁሉ ለችግሮች ማቃለያ የሚሆን ብልሃት ያቀርቡልኝ ይመስል ትክ ብዬ አየኋቸው:: ሆኖም ከበድን መልስ የለምና አፍጥጨ ቀረሁ። ሳላስበው ከቤት ወጣ ብዬ ቆምኩ፡፡ የማለዳዋ ፀሐይ ደጋናማ ጉዞዋን ጀምራለች፡፡ ደመና የማይታይበትን ሰማይ ትኩር ብሎ ላየው ኣስፈሪነቱ አይጣል! ዘልዓለም የሚሉት ይህን ርቀትና
ጥልቀት ይሆን? አንጋጥጬ ስመለከት ሐሳብ አሽቆልቁሎ አየኝ፡፡ አካባቢዬን ፈራሁት፡፡ ጥቂት ርምጃ ተራምጄ ግቢው መኻል ተገተርኩ፡፡ ከመሬት ውስጥ
መልስ ይፈልቅልኝ ይመስል ደቃቁን አፈርና ኮረት ባይኔ ሰለልኩት። ቀዝቃዛና ለስላሳ ትንሽ እጅ የቀኝ እጄን ከበስተኋላዬ ስትነካው ከፍዘቴ ነቃሁ። ጋሻዬነህን እጁን ስቤ ወደፊት አዞርኩት፡፡ ከፍ ብለው የሚበርሩ አዕዋፋትን እንደሚከታተል
ወፍ ጠባቂ ዐይኖቼን አሻቅቦ ከፈለገ በኋላ ና ቶሎ! አሁኑኑ ና ቶሎ ብላሃለች እማማዬ» ብሎ መልሴን ለመስማት ኣፉን እንደ ከፈተ ዝም አለ፡፡ ከቁመቱ ጋር ለማስተካከል ጉልበቴን አጥፈ ቁጢጥ አልኩና፣ እኔን ነው እማማዬህን ነው የምትወደው ጋሻዬነህ?» አልኩት።ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ የደብር ጉልላት የሚመስሉት ዐይኖቹ በሰፊው ተከፈቱ። «አንተንም እማማዬንም እወዳችኋለሁ...ያንን ቀይ ሽጉጥ እገዛልሃለሁ አላልከኝም ነበር፡ መቼ ትገዛልኛለህ?» ብሎ ዐይን ዐይኔን ሲያይ ዐይኖቹ በዐይኖቼ ውስጥ ሠረጉ፡፡ ትልቋ እማማስ እዚያ ትልቁ ቤት ውስጥ ያየሃቸው
የእኔ እናት አያትህ ጥሩ ናቸው? በል እስኪ ንገረኝ፡ ያንን ሽጉጥ እንድገዛልህ?»አልኩት። ከንፈሩን ትንሽ ሾል ካደረገ በኋላ «እሳቸው ደግሞ በጣም ደስ ሊሉኝ፡
ጥሩ ናቸው፡፡ ያንተ እማማ ናቸው እንዴ? እወዳቸዋለሁ» ካለ በኋላ ትልቅ በመሆኔ ከእናት ያልተወለድኩ ይመስል አወጣጧ የምታምር ሞንሟና ሣቅ ሣቀ።
«እስኪ ትወደኝ እንደሆነ ሳመኝ?» አልኩት፡፡ ጉንጩን ተራ በተራ ሳመ። «ኧረ እባካችሁ ኑ ግቡ! እባትና ልጅ ምን ትማከራላችሁ? እኔ እንዳልሰማችሁ ነው?» የሚል ድምፅ ከወደ ቤት ተሰማ፡፡ የወዲያነሽ ፍቅራዊ ትእዛዝ ስለሆነብኝ ጋሻዬነህን ይዤ ገባሁ፡፡ ቁርስ ይዛ ከተፍ አለች፡፡ የጀመረችውን ሥራ ለመዉረስ
መለስ ስትል «በይ አንሺና ይዘሽው ሂጂ!» ብዩ የካንገት በላይ ቁጣን በሚገልጽ
ስሜት ተናገርኩ፡፡ ደንገጥ ብላ ተመለሰችና «ምነው? ምን አጠፋሁ? የት ልሄድ
ነው? እደርሳለሁ ብዬ ነው ! » በማለት በፍርሃት ሳይሆን በፍቅራዊ ስሜት ትኩር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....ጋሻዬነህ ከእናቴ ጋር ውሉ አደረ፡፡ የየወዲያነሽ የእናትነት አንጀት በናፍቆት ተላወሰ፡፡ ሮብ ጧት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን «ምነው ዝም አልክ ጌታነህ? ረሳኸው እንዴ? ከጋሼ ጉልላት ጋር ምን ምን ነበር የተባባላችሁት?
ሂድና አምጣው እንጂ» አለችኝ፡፡
“ምናልባት ዛሬ የውብነሽ ታመጣው ይሆናል» አልኩና እንደገና ደግሞ
«ምናለባት ጋሻዬነህን ለእነርሱ ብንሰጣቸውና እኔና አንቺ ደግሞ….ሌላ» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ደረቷን ሁለት ጊዜ በጥፊ ደቃችና «ህ! እንዴት ያለህው ዓለመኛ ነህ! ምነው ምን በወጣኝ! ዕድሜ ላንተ እያልኩ ዐይን ዐይኑን እንዳላይ ነው!» ብላ ከነጥርጣሬዋ ዝም አለች።
ሐሳብን ማሻሻልና ፈጽሞም መለወጥ አንድ ዐይነት ዕድገት በሆኑ የሐሳቧ መለወጥና ተቃውሞዋ ደስ አለኝ፡፡ ለጥያቄዋ መልስ ሳልሰጥ ወደ ሥራ ሄድኩ፡፡
የውብነሽ ቀንም ሆነ ማታ ብቅ ሳትል ቀረች፡፡ የሮብ ጀንበር ጠልቃ የሐሙሷ ተወለደች፡፡ አዲሱ የፍርሃት ሸክም ከየወዲያነሽ ይልቅ እኔን ከበደኝ፡፡ ከማታ
ትምህርት መልስ ሻይ እየጠጣን ስናወራ አንዱን ተረስቶ የቀረ የጋሻዬነህን የሒሳብ ደብተር እያገላበጠች «እሷ መች ሥራ አጣችና ነው ይዛው ትመጣለች
የምትለው? እኔ እኮ ነገሩ የገባኝ የመማሪያ ደብተሩን ይዛ ስትሒድ ነው» ብላ ወደ ራሷ ደብተሮች መለስ አለች፡፡
«እኔን ያሠጋኝ ሌላው አይደለም.....አባባ ይመለሳል ከተባለበት ቀን ቀደም ብሎ ቢመለስና ይኸ ልጅ የማን ነው ልጅ? ብሎ ቢጠየቅ ምን ይላሉ?
እናቴ ገና እንማከራለን ነው ያለችኝ እንጂ ሌላ የተነጋገርነው ነገር የለም ከማለቴ፣ የማን ልጅ እንዲባልልህ ትፈልጋለህ? የጌታነህ ልጅ ነው ብለው
ይነግሩልሃላ» ብላ ኩታ አጣፍቶ የመልበስ ያህል ጉዳዩን አቃልላ መለሰችልኝ።
«እንዴት አንቺ? እኔ እኮ ገና ብዙ ግብግብና ትግል ይጠብቀኛል።
የሙሉ ድሌ ቀኔ ገና ነው:: ምኑ ተያዘና!ምኑ ተነካና! እንዴት አድርጌ እንደምገጥመውና ድል እንደማደርገው ዕቅድና ብልሃቴ አልተጠናቀቀም፡፡ወደፊት የሚቀረኝ የትግል ጉራንጉር ያለፉትን የመከራና የትግል ገድሎች ሁሉ ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ ቀሪው ትግል በዕድልና በአጋጣሚ የማምንበት ነገር
የለም፡፡ የሚጠብቀኝ ውጣ ውረድ ሁሉ በበቂ ምክንያትና በተግባር የሚመራ ነው። «የዘልማድ ዝላይና ባወጣ ያውጣኝ በቃው! በቂ ምክንያት ጥሩ የተግባር
ዋስትና» ብዬ በመጀመር ለወደፊት ከሚያጋጠሙኝ አንደንድ ችግሮች መኻል አንዳንዶቹን በከፊል አዋየኋት፡፡
ዓርብ ከጧቱ ሁለት ሰዓት ላይ የውብነሽ ጋሻዬነህን ይዛ መጣች።
የሚያምር አዲስ ልብስ ለብሶ
ከፈገግታው ጋር ሲታይ የመስከረም ዝናብ ያጠባት
የለጋ ዘንባባ ተክል መስሏል። የወዲያነሽ ግልገሏን አስከትላ ጢሻ ውስጥ እንደምትገባ ሰስ ልጅዋን አስከትላ ወደ ጓዳ ገባች። እኔና የውብነሽ ወጣ ብለን ሰበሰቡ ላይ እንደቆምን «አባባ የነገ ሳምንት ከሰዓት በኋላ ይገባል፡፡ ባለቢትህን እንዴት አድርገን እሱ ፊት እንደምናቀርባት፡ አንተም ምንና ምን እያልክ መናገርና ማስረዳት እንዳለብህ አንድ ባንድ አውጥተን አውርደን ጨርሰናል» ብላ ስለ እኛ ሕይወት እኔና ባለቤቴ ያልተካፈልንበትን የአፈጻጸም ዕቅድ አረዳችኝ፡፡
የችግሬን ዐይነትና ዓላማዬን የማውቀው እኔ ሆኜ ሳለሁ መወከልና ማስፈጸም
የማይገባቸው እኅቴና እናቴ አፈ ቀላጤ ሆነን እንገኝ ሲሉ በመስማቴ ተናደድኩ፡፡
አልተዋጠልኝም፡፡
የአባቴ ግብዝነትና ቁጣዉ፣ ግትርነቱንና የመጣ ይምጣ ባይነቱ፣ እንደ ጨካኝ አገረ ገዢ ፊት ለፊት ቆሞ እንደ እሳት ፈጀኝ፡፡ «ማታ ከትምህርት ቤት
መልስ ከየወዲያነሽ ጋር እንድትመጡ፣ ነገሩን አብራራልሃለሁ። አሁን ግን
ቸኩያለሁ ደኀና ዋል» ብላኝ ቶሉ ብለህ ና እንደ ተባለ መልእክተኛ ጥላኝ ሄደች። አእምሮዬ በሐሳብ ተወቃ፡፡ ሁለመናዬ ብው ብሎ ጋመ፡፡ አዳዲስ ጭንቀቶች በውስጤ ተራወጡ፡፡ የሐሳቤ አድማስ ለመጥበብም ሆነ ለመስፋት ባለመቻሉ መረጋጊያ አጣሁ፡፡
ጎርፍ እንደ ገረሰሰው ዛፍ ግድግዳውን ተደግፌ ቆምኩ፡፡ የወዲያነሽ ከወደ ውስጥ መጥታ «ከምን ጊዜው ሄደች? ያንተ ነገር እኮ...አናደድካት እንዴ?» ብላ
በሥጋት አዘል ሁኔታ ጠየቀችኝ፡፡ «ቸኩላ ነበር፡ ታናድደኛለች እንጂ ምን አናድዳታለሁ፡፡ የማይጠቅሙሽ እጠቅምሻለሁ፣ የሚያጠፉሽ አለማሻለሁ፣
የሚገድሉሽ አድንሻለሁ ሲሉሽ አትናደጂም? አሁን የነገረችኝን ማታ ስትነግረኝ ትሰሚያታለሽ፡፡ አሁን ወደ ሥራሽ ሂጂ» ብያት ዝም አልኩ፡፡ የእርሷ ከአጠገቤ
ገለል ማለት የሚረዳኝ ስለ መሰላት ተመልሳ ገባች፡፡ በአካባቢዬ የሚገኙት ነገሮች
ሁሉ ለችግሮች ማቃለያ የሚሆን ብልሃት ያቀርቡልኝ ይመስል ትክ ብዬ አየኋቸው:: ሆኖም ከበድን መልስ የለምና አፍጥጨ ቀረሁ። ሳላስበው ከቤት ወጣ ብዬ ቆምኩ፡፡ የማለዳዋ ፀሐይ ደጋናማ ጉዞዋን ጀምራለች፡፡ ደመና የማይታይበትን ሰማይ ትኩር ብሎ ላየው ኣስፈሪነቱ አይጣል! ዘልዓለም የሚሉት ይህን ርቀትና
ጥልቀት ይሆን? አንጋጥጬ ስመለከት ሐሳብ አሽቆልቁሎ አየኝ፡፡ አካባቢዬን ፈራሁት፡፡ ጥቂት ርምጃ ተራምጄ ግቢው መኻል ተገተርኩ፡፡ ከመሬት ውስጥ
መልስ ይፈልቅልኝ ይመስል ደቃቁን አፈርና ኮረት ባይኔ ሰለልኩት። ቀዝቃዛና ለስላሳ ትንሽ እጅ የቀኝ እጄን ከበስተኋላዬ ስትነካው ከፍዘቴ ነቃሁ። ጋሻዬነህን እጁን ስቤ ወደፊት አዞርኩት፡፡ ከፍ ብለው የሚበርሩ አዕዋፋትን እንደሚከታተል
ወፍ ጠባቂ ዐይኖቼን አሻቅቦ ከፈለገ በኋላ ና ቶሎ! አሁኑኑ ና ቶሎ ብላሃለች እማማዬ» ብሎ መልሴን ለመስማት ኣፉን እንደ ከፈተ ዝም አለ፡፡ ከቁመቱ ጋር ለማስተካከል ጉልበቴን አጥፈ ቁጢጥ አልኩና፣ እኔን ነው እማማዬህን ነው የምትወደው ጋሻዬነህ?» አልኩት።ፊቱ በፈገግታ ፈክቶ የደብር ጉልላት የሚመስሉት ዐይኖቹ በሰፊው ተከፈቱ። «አንተንም እማማዬንም እወዳችኋለሁ...ያንን ቀይ ሽጉጥ እገዛልሃለሁ አላልከኝም ነበር፡ መቼ ትገዛልኛለህ?» ብሎ ዐይን ዐይኔን ሲያይ ዐይኖቹ በዐይኖቼ ውስጥ ሠረጉ፡፡ ትልቋ እማማስ እዚያ ትልቁ ቤት ውስጥ ያየሃቸው
የእኔ እናት አያትህ ጥሩ ናቸው? በል እስኪ ንገረኝ፡ ያንን ሽጉጥ እንድገዛልህ?»አልኩት። ከንፈሩን ትንሽ ሾል ካደረገ በኋላ «እሳቸው ደግሞ በጣም ደስ ሊሉኝ፡
ጥሩ ናቸው፡፡ ያንተ እማማ ናቸው እንዴ? እወዳቸዋለሁ» ካለ በኋላ ትልቅ በመሆኔ ከእናት ያልተወለድኩ ይመስል አወጣጧ የምታምር ሞንሟና ሣቅ ሣቀ።
«እስኪ ትወደኝ እንደሆነ ሳመኝ?» አልኩት፡፡ ጉንጩን ተራ በተራ ሳመ። «ኧረ እባካችሁ ኑ ግቡ! እባትና ልጅ ምን ትማከራላችሁ? እኔ እንዳልሰማችሁ ነው?» የሚል ድምፅ ከወደ ቤት ተሰማ፡፡ የወዲያነሽ ፍቅራዊ ትእዛዝ ስለሆነብኝ ጋሻዬነህን ይዤ ገባሁ፡፡ ቁርስ ይዛ ከተፍ አለች፡፡ የጀመረችውን ሥራ ለመዉረስ
መለስ ስትል «በይ አንሺና ይዘሽው ሂጂ!» ብዩ የካንገት በላይ ቁጣን በሚገልጽ
ስሜት ተናገርኩ፡፡ ደንገጥ ብላ ተመለሰችና «ምነው? ምን አጠፋሁ? የት ልሄድ
ነው? እደርሳለሁ ብዬ ነው ! » በማለት በፍርሃት ሳይሆን በፍቅራዊ ስሜት ትኩር
👍6
#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አስታውሳለሁ ግን እኮ ታዲያ...” ብዩ ሙሉ ሐሳቤን ሳልገልጽላት ዝም አልኩ።የዝምታዬ መነሾና ጥጥር ምክንያት ግን አዲሱ እኔ በመሆኑ እሷ ልታውቀው
አትችልም፡፡
«ና በል እንሒድ ቶሉ እንመለሳለን» አለችና ተነሣች። የእኔ ጉዳይ
በእርሷና በእናቴ መካከል ተመክሮበት ያለቀ በመሆኑ እንግዲህ አደራሽን እንደዚያቹ እንደ ምክራችን አድርገሽ ንገሪው፡፡ እኔና አንቺ እንደ ተባባልነው
ቢሆን ይሻላል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ እኔ ደኅና አድርጌ እነግረዋለሁ፤ አደራሽን አደራችሁን» ብላ እናቴ በዐይኗ ሸኘችኝ፡፡ «ሂዱ» የምትለን ወደ እኔ ቤት መሆኑን አወቅሁ፡፡ የወዲያነሽን ለመጠበቅ ቆምኩ። «ሂዱ እንጂ ምን ቀረህ?
እናቷ እኮ ነኝ! ሌላ እናት ያላት መሰለህ? አይዞህ! ለሌላ ሰው አልሰጥብህም፣ እሷም በጀ አትልም» ብላ ስቃ አሣቀችኝ፡፡ የወዲያነሽ እናቴን በዐይኗ እየጠበቀች 'የሂዱ' ምልክት በጣቷ አሳየችኝ። ምርቱን እንደከተተ ሰው ተደስቼ ወጣሁ፡፡ወደ እኔ ቤት የመሄዱን ነገር ሰርዘን መኪና ውስጥ ተቀመጥን።
«አባቴ ስለ አንተና ስለ የወዲያነሽ ምንም ነገር ፈጽሞ እንዳልሰማና እስከ ዛሬም እንዳላወቀ ታውቃለህ:: ምስጢሩን የቀበርነው ሁላችንም ስለ ፈራነው ነው»
በማለት ንግግሯን ጀመረች፡፡ ጠንቃቃነቴንና ለጉዳዩ ያለኝን ከፍተኛ ግምት በግልጽ ለማስረዳት «አንቺና እማማስ ብትሆኑ ካባረራችኋት በኋላ ስለ እርሷ ምን የምታውቁት ነገር ነበር? ምስጢሩ ያልተነዛው ከእርሷ ጋር በመባረሩና እስር ቤት
በመውረዱ ነበር» ብዩ ተራ ለቀቅሁ፡፡
«ነገሩን በብልሃትና በዘዴ ካላስኬድነው በስተቀር ከአባታችን ጋር ብዙ ንትርክና ጭቅጭቅ እንደሚነሳ የታወቀ ነው፡፡ እኛ ግን ስለ ነገሩ ፍንጭ አግኝቶ
እንዲጠራጠር በማድረግ ጉዳዩን ለመጀመር አስበናል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ አንተም እኛም ጥሩ ጥሩ ሽማግሌዎች መርጠን...» ብላ ሳትጨርስ «የብልሃቴ አቀነባባሪ እኔ ነኝ፡፡ የአዲሱ ሕይወቴ ጎዳና ቀያሽና ደልዳይ ራሴ ነኝ።
እያስፈልግም፡ በቃኝ! አባቴንም እንደ እናቴ በማስማልና በፍርሃት
እየተርበደበድኩ በመጠጋት የሚለኝንና የሚወስንብኝን ሁሉ አቀርቅሬ በመስማት ዕድል ለሚሏት አጋጣሚ ነገር አልንበረከክም! መጠራጠር ማለት ስለ አንድ ነገር ቢያንስ በጥቂቱ ማወቅ ወይም መገመት ማለት ነው። የትላንቱን ስሕተቴን ዛሬና
ነገ መድገም የለብኝም፡፡ አታስቡ! እኔ ለአባቴ የራሴ ዝግጅት አለኝ፡፡ በቀጥታ ቀርቤ ፊት ለፊት አስረዳዋለሁ፡፡ ለጥያቄዎቹም መልስ እሰጣለሁ» በማለት ጣልቃ
ገብቼ ተናገርኩ። ድንገት ደሟ ፈላና «ከንትርክና ብዙ ጣጣን ከሚያስከትል ጭቅጭቅ ይልቅ መግባባት ይበልጣል። በንትርክና በአሻፈረኝ ባይነት የምታገኘው
ድል አድራጊነት ሁሉ እስከ መጨረሻው አያረካህም፡፡ አባቴ በመጀመሪያ ጋሻዬነን አይቶ ከተደሰተና የሐሳቡ አቅጣጫ ካማረ ሁሉም ነገር ይሳካልናል።
የወዲያነሽንና የአንተን ግንኙነት፣ የደረሰባትን መከራና ሥቃይ ሁሉ ቀስ በቀስ እተርክለታለሁ፡፡ ልቡ ካዘነና መንፈሱ በርህራሄ ከተነካ፡ በሉ ሂዱና አምጧት ይላል” ብላ ነገሯን ልታራዝም ስትል «አይቻልም! ማን አስተርጓሚ አደረገሽና!
መሸሸግም ሆነ መደበቅ የለበትም፡፡ አልለማመጥም:: እጅግ አርኪው ድል አድራጊነትም ከትግልና ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ ድል አድራጊነት ነው፡፡ እኔና
የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አስከትለን ባንድ ላይ እንቀርባለን፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት “እንቺም ሆንሽ እናቴ አንዲት ቃል መናገርም ሆነ ማሰማት የለባችሁም፡፡ በምንቀርብበት ቀን እንግዶች ቢኖሩም ባይኖሩም ግድ የለኝም። እንዲያውም ወሬው እንዲስፋፋና እንዲዛመት ብዙ ሰዎች ቢኖሩ በጣም ጥሩ ነው:: በዚህ ብትስማሙ ተስማሙ፡ አለበለዚያ ግን የማደርገውንና የማላደርገውን እኔ ራሴ አውቃለሁ፡፡ እኔ የምፈልገው እንዲያውቅ ብቻ እንጂ እንዲስማማ ወይም መርቆ
እንዲቀበለን አይደለም፡፡ ከባለቤቴ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ አስተያየትም ሆነ ሌላ ሐሳብ እንዲያቀርብ አይደለም» በማለት ቀጥ እንዳለ አቀበት ስትፈራው የቆየችውን ጉዳይ አውላላ ሜዳ አደረግሁላት፡፡ በእኔ ላይ የነበራት ግምትና አስተሳሰብ ሁሉ ነፋስ እንደ መታው ልም ዱቄት ተበተነ፡፡በሁለታችን መካከል በጣም ግዙፍ የሆነ የሐሳብ ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በእኔ ላይ የሐሳብ በላይነት ለማግኘት ባለመቻሏ ተከዘች። ምክራቸውንና መላቸውን ሁሉ ባለምቀበሌ ንዴቷ ናረ። የመዥገር ሞት ያህል አላሳዘነችኝም፡፡ ቁርጡን ለማወቅ
የጓጓው አእምሮዋ ራሱ የዘጋውን የዝምታ በር ከፈተው፡፡ «እኔ እና የግሌን የአቀራረብ መንገድና ሐሳብ አዘጋጃለሁ እንጂ የእናንተን አልቀበልም ማለትህ ነው?» ብላ ሁኔታዬንም አብራ ለመረዳት ፊቷን ወደ እኔ አዞረች፡፡
ባጭሩና በቀላሉ ”አዎ” አልኩና ተጨማሪ ምክንያትና ማብራሪያ
ለማቅረብ ስዘጋጅ «በቃኝ አያስፈልገኝም! አልሰማም ቀኙን ሲያሳዩህ ግራ ግራውን ትመርጣለህ፡፡ እኔን ያናደደኝ ያንተ እምቢታና የመጣው ይምጣ ባይነት ሳይሆን በዚሀ ይሻላል በዚያ፡ ይኸ ያዋጣል ያኛው ይበልጣል እያልኩ ከእናቴ ጋር
ስነታረክና ስከራከር መሰንበቴ ነው» ብላ ፊቷን አዞረች።
አልደነገጥኩም፡፡ «የአንቺም ይሁን የእናቴ ርዳታ እያስፈልገኝም፡፡ ጥገና እና ድረታ አልፈልግም፡ ጥገና አይዋጥልኝም! ጥገና ማለት ውስጠ ሰባራ ማለት ነው፡፡
ከሆነላችሁ እናንተም ተደርባችሁ በጥያቄና መልስ አዋከቡኝ! ዝግጁ ነኝ። ነገር ግን እኔ በማልገኝበት ወቅት አባቴን እንድትለምኑልኝና እኔን፣ ባለቤቴንና ልጄን ዝቅ አድርጋችሁ እንድትለማመጡልኝ አልፈልግም፡፡ እኔ ራሴ ባለጉዳዩ ፍላጎቴንና ውሳኔዩን ለማስረዳት በሚገባ ዝግጁ ሆኛለሁ» ብዬ ፋታ ሰጠሁ፡፡
«አያዋጣም እንጂ ቢያዋጣማ ጥሩ ነው:: ለፍተህ ለፍተህ እዚህ ከደረስክ በኋላ እንዴት እንዲህ በቀላሉ ትገነፍላለህ?» ብላ ራሷን ነቀነቀች።
«በቃኝ ነው የምልሽ! በሐሳቤና በእምነቴ እንድትስማሚ አላስገድድሽም። የገዛ መብቴን አልመፀወትም:: የሕሊናዬን ቁስል የማድንበትን መድኃኒት ቀስ በቀስ እያወቅሁ ነው:: ከአባቴ መሠረተቢስ እምነት ጋር እንድጋጭና እንድታተር
እንጂ እንደ ከዚህ ቀደሙ አንገቴን ሰብሬ የሚኖረው የሚያቀርበውን
ዝባዝንኪ ሐሳብ ሁሉ ያለ አንዳች ክርክር እንድቀበል አልፈልግም! ጨቋኝ ግዴታውን አልቀበልም:: ሐሳባችሁንም ሰርዙ። ከዚህ አሁን ከነገርኩሽ አፈጻጻም ውጪ አንዳችም የምቀበለውና የምስማማበት ሐሳብ ስለ ሌለ ነገር ሳናንዛዛ ወደ ቤት እንግባ» አልኩና ለጠላቱ የመጭረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጥ
ሰው የማያወላዳውን ነገርኳት። ለወለላ ገሥግላ ፊት ዛቀች!
ያለውን ይበል ብላ እንዴት አታስብም? እንዴት አይገባህም? ነገሩን ረጋ ብለህ ተመልከተው፡ ራስህን ብቻ አትውደድ፡ ይኸማ ይበጣበጡ' ይጣሉ፡ ይጋደሉ ማለትህ እኮ ነው? ስንትና ስንት ዓመት ሙሉ ምስጢሩን ደብቀህ
ከኖርክ በኋላ አሁን በመጨረሻ ጣጣን አመጣህ። ለካስ በጄም በግሬም ገብተህ የተለማመጥከኝ እንዲህ ለመሆን ኖሯል? አሁን አንተ በምትለው ሁኔታ ከሆነ
አገር ምድሩን እንደሚበጠብጥ አውቃለሁ፡፡ እናቴ ግን ያን ሁሉ አድራጎት ያደረገችው ላንተው ስትል እንደነበር ታውቃለህ» ብላ ፊት ለፊት ወደ ጨለማው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አስታውሳለሁ ግን እኮ ታዲያ...” ብዩ ሙሉ ሐሳቤን ሳልገልጽላት ዝም አልኩ።የዝምታዬ መነሾና ጥጥር ምክንያት ግን አዲሱ እኔ በመሆኑ እሷ ልታውቀው
አትችልም፡፡
«ና በል እንሒድ ቶሉ እንመለሳለን» አለችና ተነሣች። የእኔ ጉዳይ
በእርሷና በእናቴ መካከል ተመክሮበት ያለቀ በመሆኑ እንግዲህ አደራሽን እንደዚያቹ እንደ ምክራችን አድርገሽ ንገሪው፡፡ እኔና አንቺ እንደ ተባባልነው
ቢሆን ይሻላል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ እኔ ደኅና አድርጌ እነግረዋለሁ፤ አደራሽን አደራችሁን» ብላ እናቴ በዐይኗ ሸኘችኝ፡፡ «ሂዱ» የምትለን ወደ እኔ ቤት መሆኑን አወቅሁ፡፡ የወዲያነሽን ለመጠበቅ ቆምኩ። «ሂዱ እንጂ ምን ቀረህ?
እናቷ እኮ ነኝ! ሌላ እናት ያላት መሰለህ? አይዞህ! ለሌላ ሰው አልሰጥብህም፣ እሷም በጀ አትልም» ብላ ስቃ አሣቀችኝ፡፡ የወዲያነሽ እናቴን በዐይኗ እየጠበቀች 'የሂዱ' ምልክት በጣቷ አሳየችኝ። ምርቱን እንደከተተ ሰው ተደስቼ ወጣሁ፡፡ወደ እኔ ቤት የመሄዱን ነገር ሰርዘን መኪና ውስጥ ተቀመጥን።
«አባቴ ስለ አንተና ስለ የወዲያነሽ ምንም ነገር ፈጽሞ እንዳልሰማና እስከ ዛሬም እንዳላወቀ ታውቃለህ:: ምስጢሩን የቀበርነው ሁላችንም ስለ ፈራነው ነው»
በማለት ንግግሯን ጀመረች፡፡ ጠንቃቃነቴንና ለጉዳዩ ያለኝን ከፍተኛ ግምት በግልጽ ለማስረዳት «አንቺና እማማስ ብትሆኑ ካባረራችኋት በኋላ ስለ እርሷ ምን የምታውቁት ነገር ነበር? ምስጢሩ ያልተነዛው ከእርሷ ጋር በመባረሩና እስር ቤት
በመውረዱ ነበር» ብዩ ተራ ለቀቅሁ፡፡
«ነገሩን በብልሃትና በዘዴ ካላስኬድነው በስተቀር ከአባታችን ጋር ብዙ ንትርክና ጭቅጭቅ እንደሚነሳ የታወቀ ነው፡፡ እኛ ግን ስለ ነገሩ ፍንጭ አግኝቶ
እንዲጠራጠር በማድረግ ጉዳዩን ለመጀመር አስበናል፡፡ ከዚያ በኋላ ደግሞ አንተም እኛም ጥሩ ጥሩ ሽማግሌዎች መርጠን...» ብላ ሳትጨርስ «የብልሃቴ አቀነባባሪ እኔ ነኝ፡፡ የአዲሱ ሕይወቴ ጎዳና ቀያሽና ደልዳይ ራሴ ነኝ።
እያስፈልግም፡ በቃኝ! አባቴንም እንደ እናቴ በማስማልና በፍርሃት
እየተርበደበድኩ በመጠጋት የሚለኝንና የሚወስንብኝን ሁሉ አቀርቅሬ በመስማት ዕድል ለሚሏት አጋጣሚ ነገር አልንበረከክም! መጠራጠር ማለት ስለ አንድ ነገር ቢያንስ በጥቂቱ ማወቅ ወይም መገመት ማለት ነው። የትላንቱን ስሕተቴን ዛሬና
ነገ መድገም የለብኝም፡፡ አታስቡ! እኔ ለአባቴ የራሴ ዝግጅት አለኝ፡፡ በቀጥታ ቀርቤ ፊት ለፊት አስረዳዋለሁ፡፡ ለጥያቄዎቹም መልስ እሰጣለሁ» በማለት ጣልቃ
ገብቼ ተናገርኩ። ድንገት ደሟ ፈላና «ከንትርክና ብዙ ጣጣን ከሚያስከትል ጭቅጭቅ ይልቅ መግባባት ይበልጣል። በንትርክና በአሻፈረኝ ባይነት የምታገኘው
ድል አድራጊነት ሁሉ እስከ መጨረሻው አያረካህም፡፡ አባቴ በመጀመሪያ ጋሻዬነን አይቶ ከተደሰተና የሐሳቡ አቅጣጫ ካማረ ሁሉም ነገር ይሳካልናል።
የወዲያነሽንና የአንተን ግንኙነት፣ የደረሰባትን መከራና ሥቃይ ሁሉ ቀስ በቀስ እተርክለታለሁ፡፡ ልቡ ካዘነና መንፈሱ በርህራሄ ከተነካ፡ በሉ ሂዱና አምጧት ይላል” ብላ ነገሯን ልታራዝም ስትል «አይቻልም! ማን አስተርጓሚ አደረገሽና!
መሸሸግም ሆነ መደበቅ የለበትም፡፡ አልለማመጥም:: እጅግ አርኪው ድል አድራጊነትም ከትግልና ከሥቃይ በኋላ የሚገኝ ድል አድራጊነት ነው፡፡ እኔና
የወዲያነሽ ጋሻዬነህን አስከትለን ባንድ ላይ እንቀርባለን፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት “እንቺም ሆንሽ እናቴ አንዲት ቃል መናገርም ሆነ ማሰማት የለባችሁም፡፡ በምንቀርብበት ቀን እንግዶች ቢኖሩም ባይኖሩም ግድ የለኝም። እንዲያውም ወሬው እንዲስፋፋና እንዲዛመት ብዙ ሰዎች ቢኖሩ በጣም ጥሩ ነው:: በዚህ ብትስማሙ ተስማሙ፡ አለበለዚያ ግን የማደርገውንና የማላደርገውን እኔ ራሴ አውቃለሁ፡፡ እኔ የምፈልገው እንዲያውቅ ብቻ እንጂ እንዲስማማ ወይም መርቆ
እንዲቀበለን አይደለም፡፡ ከባለቤቴ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ አስተያየትም ሆነ ሌላ ሐሳብ እንዲያቀርብ አይደለም» በማለት ቀጥ እንዳለ አቀበት ስትፈራው የቆየችውን ጉዳይ አውላላ ሜዳ አደረግሁላት፡፡ በእኔ ላይ የነበራት ግምትና አስተሳሰብ ሁሉ ነፋስ እንደ መታው ልም ዱቄት ተበተነ፡፡በሁለታችን መካከል በጣም ግዙፍ የሆነ የሐሳብ ልዩነት ተፈጠረ፡፡ በእኔ ላይ የሐሳብ በላይነት ለማግኘት ባለመቻሏ ተከዘች። ምክራቸውንና መላቸውን ሁሉ ባለምቀበሌ ንዴቷ ናረ። የመዥገር ሞት ያህል አላሳዘነችኝም፡፡ ቁርጡን ለማወቅ
የጓጓው አእምሮዋ ራሱ የዘጋውን የዝምታ በር ከፈተው፡፡ «እኔ እና የግሌን የአቀራረብ መንገድና ሐሳብ አዘጋጃለሁ እንጂ የእናንተን አልቀበልም ማለትህ ነው?» ብላ ሁኔታዬንም አብራ ለመረዳት ፊቷን ወደ እኔ አዞረች፡፡
ባጭሩና በቀላሉ ”አዎ” አልኩና ተጨማሪ ምክንያትና ማብራሪያ
ለማቅረብ ስዘጋጅ «በቃኝ አያስፈልገኝም! አልሰማም ቀኙን ሲያሳዩህ ግራ ግራውን ትመርጣለህ፡፡ እኔን ያናደደኝ ያንተ እምቢታና የመጣው ይምጣ ባይነት ሳይሆን በዚሀ ይሻላል በዚያ፡ ይኸ ያዋጣል ያኛው ይበልጣል እያልኩ ከእናቴ ጋር
ስነታረክና ስከራከር መሰንበቴ ነው» ብላ ፊቷን አዞረች።
አልደነገጥኩም፡፡ «የአንቺም ይሁን የእናቴ ርዳታ እያስፈልገኝም፡፡ ጥገና እና ድረታ አልፈልግም፡ ጥገና አይዋጥልኝም! ጥገና ማለት ውስጠ ሰባራ ማለት ነው፡፡
ከሆነላችሁ እናንተም ተደርባችሁ በጥያቄና መልስ አዋከቡኝ! ዝግጁ ነኝ። ነገር ግን እኔ በማልገኝበት ወቅት አባቴን እንድትለምኑልኝና እኔን፣ ባለቤቴንና ልጄን ዝቅ አድርጋችሁ እንድትለማመጡልኝ አልፈልግም፡፡ እኔ ራሴ ባለጉዳዩ ፍላጎቴንና ውሳኔዩን ለማስረዳት በሚገባ ዝግጁ ሆኛለሁ» ብዬ ፋታ ሰጠሁ፡፡
«አያዋጣም እንጂ ቢያዋጣማ ጥሩ ነው:: ለፍተህ ለፍተህ እዚህ ከደረስክ በኋላ እንዴት እንዲህ በቀላሉ ትገነፍላለህ?» ብላ ራሷን ነቀነቀች።
«በቃኝ ነው የምልሽ! በሐሳቤና በእምነቴ እንድትስማሚ አላስገድድሽም። የገዛ መብቴን አልመፀወትም:: የሕሊናዬን ቁስል የማድንበትን መድኃኒት ቀስ በቀስ እያወቅሁ ነው:: ከአባቴ መሠረተቢስ እምነት ጋር እንድጋጭና እንድታተር
እንጂ እንደ ከዚህ ቀደሙ አንገቴን ሰብሬ የሚኖረው የሚያቀርበውን
ዝባዝንኪ ሐሳብ ሁሉ ያለ አንዳች ክርክር እንድቀበል አልፈልግም! ጨቋኝ ግዴታውን አልቀበልም:: ሐሳባችሁንም ሰርዙ። ከዚህ አሁን ከነገርኩሽ አፈጻጻም ውጪ አንዳችም የምቀበለውና የምስማማበት ሐሳብ ስለ ሌለ ነገር ሳናንዛዛ ወደ ቤት እንግባ» አልኩና ለጠላቱ የመጭረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሚሰጥ
ሰው የማያወላዳውን ነገርኳት። ለወለላ ገሥግላ ፊት ዛቀች!
ያለውን ይበል ብላ እንዴት አታስብም? እንዴት አይገባህም? ነገሩን ረጋ ብለህ ተመልከተው፡ ራስህን ብቻ አትውደድ፡ ይኸማ ይበጣበጡ' ይጣሉ፡ ይጋደሉ ማለትህ እኮ ነው? ስንትና ስንት ዓመት ሙሉ ምስጢሩን ደብቀህ
ከኖርክ በኋላ አሁን በመጨረሻ ጣጣን አመጣህ። ለካስ በጄም በግሬም ገብተህ የተለማመጥከኝ እንዲህ ለመሆን ኖሯል? አሁን አንተ በምትለው ሁኔታ ከሆነ
አገር ምድሩን እንደሚበጠብጥ አውቃለሁ፡፡ እናቴ ግን ያን ሁሉ አድራጎት ያደረገችው ላንተው ስትል እንደነበር ታውቃለህ» ብላ ፊት ለፊት ወደ ጨለማው
👍3
#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ሰኞና ማክሰኛ ተከታታዮቹም ቀናት በየተራ አልፈው ቅዳሜ ደረሰ፡፡ሁላችንም በሐሳባችን እንደ ጸናን ሰነበትን
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ዘጠኝ ተኩል ገደማ ላይ ደርሶ ብርድ ብርድ ስላለኝ ፀሐይ ለመሞቅ ምድረ ግቢው መኻል ተቀመጥኩ በየወዲያነሽ አእምሮ ውስጥ
ያለው ጥያቄ ሳይመለስ በመሰንበቱ ሥጋቷ አልተወገደም፡፡ በአንዲት ትንሽ ነጭ ፎጣ ብርጭቆ እየወለወለች ዝግ ብላ መጣችና “አሁን ነው እንዴ የምንሄደው? እ...!» ብላ ንግግሯን በጥያቄ አንጠለጠለችው::
«አንቺና ጋሻዬነህ የምትሄዱት ሌላ ጊዜ ነው:: ቀኑን እኔና አንቺ
እንወስነዋለን፡፡ ዛሬም ሆነ ነገ የምሄደው እኔ ነኝ። ከነዚያ ከተከለከሉ መጻሕፍት አንብባ የነገረችሽን የእስረኛዋን ጓደኛሽን የምክር ቃላት አትርሺ፡ መብት
የሚገኘው በትግል ነው፡፡ ጨቋኞች በሰላምና በውዴታ መብት እይሰጡም ብላ
ነግራኛለች አላልሽም? እኔና አንቺም» ብዬ ዝም አልኳት። ከጀመርኩት አርእስት ውጪ «አዎ እውነትህን ነው: ከመንገድ ሲገቡ ያላሰቡትን ያልሰሙትን ነገር ተናግሮ ክፉም ደግም መስማትና መናገር ለእርሳቸውም ሆነ
ለእኛ ነገር ማበላሸት ነው» ብላ የብርጭቆይቱን ጥራት ለማረጋገጥ ትክ ብላ ተመለከተቻት ንግግሯን ሰምቼ ዝም ስላልኩ ወደ ቤት ገባች፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አባቴን እንኳን ደኅና” መጣህ ለማለት ወደ ወላጆቼ ቤት ገሠገሥኩ፡፡
ባለፈው ጊዜ ወላጆቼን ለመጠየቅ ስሔድ ይጨመድደኝ የነበረው
ሥጋትና ፍርሃት እንዲሁም የሕሊና ረብሻ እጅግ በጣም ተቀነሰ። እረጋገጤ ደልዳላ ከመሆኑም በላይ ቀና ብዬ ተራመድኩ፡፡ ዱሮ ደረጃውን የምወጣው አንድ
በአንድ ሲሆን ዛሬ ግን ሁለትና ሦስቱን በአንድ ጊዜ አጠቃለልኩት። ደረጃውን
ጨርሼ ፊቴን ወደ በሩ መለስ ሳደርግ የብዙ ሰዎች ድምፅ ሰማሁ፡፡ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ የነበረኝ ድፍረት ከፍ አለ። እቤቱ ውስጥ ለነበሩት ሁሉ ጎንበስ ብዬ
እጅ ነሣሁ፡፡ ከዚያም በቀጥታ ወደ አባቴ ሄድኩና እጅ ነሥቼ ጨበጥኩት።
«እንኳን ደኅና ገባህ! የሄድክበት ሁሉ ቀናህ! » አልኩና አንገቴን በትሕትና ሰበር አድርጌ ከፊቱ ገለል ብዬ ቆምኩ፡፡
እንኳን ደኅና ቆያችሁኝ አዎ ደኅና ደርሼ መጣ። ሁሉም ደህና
ቆየኝ። ክብሩ ይስፋ!ና! እዚች አጠገቤ ና አጠገቡ የነበረውን ወንበር በጣቱ አሳየኝ። እንኳን በደህና ገቡ ለማለት ያመጡትንና ሌሎችንም እንግዶች አንድ
በአንድ አየኋቸው፡፡ በሰዎች ላይ የሚታየው ፈገግታና የአቀማመጣቸው ሁናቴ
የተለያየ በመሆኑ አባቴን በተለያየ የአስተሳሰብ ደረጃ እንደሚመለከቱት ያስታውቃል። አንዳንዱ ውስጣዊ ጭንቀት አስገድዶት በግድ ፈገግ ብሏል።
ለማስደሰትና በግድ ለመደሰት ብሉ በደረቅ ፈገግታ ፊቱን ያጨማደደም አለ።የአንዳንዶቹን ፊት ደግሞ የበታችነት ስሜት ስለተጫነው ፊታቸው ከልቅሶ በኋላ የሚታይ ፊት እንጂ ለደስታ የቀረበ ገጽታ አይመስልም፡፡
ሁለትና ሦስቱን እንደ አባቴ የቅርብ ጓደኞች ስለምመለከታቸው በእነርሱ ላይ የነበረኝን ጥላቻ ለመርሳትም ሆነ ለማሻሻል ያለኝ አቅም በጣም አነስተኛ ነበር። ሕሊናዬ ዘወትር ይበቀላቸዋል፡፡ ወረቀት እያገላበጡ የሚዶልቱት ሁሉ ትውስ ሲለኝ፡ የሰውን ሕልውና አርደውና አወራርደው የሚገድሉ ይመስሉኛል።
ክርክርና ወሬ ሲጀምሩ ማንም በአጠገባቸው እንዲያልፍ ስለማይፈልጉ ዓለምን
የተንኮል ገበያ እንጂ የመልካም ምግባር አደባባይ እንድትሆን የሚያስቡ አይመስሉም፡፡ እናቴ እንኳን ደበቅ እያለች «መጡ ደግሞ እነ ጋጠው ገሽልጠው»
ትላቸው ነበር፡፡
ለእኔም እንደ እንግዶቹ ጠላ ደረሰኝ፡፡ ከዚህም ከዚያም የሚመጣውን ወሬ እየሰማሁ ጠላዬን ሁለት፣ ሦስት ጊዜ አስሞላሁ፡፡ እንግዶቹ አንድና ሁለት እየሆኑ ተራ በተራ እጅ እያነሡ ሄዱ።
እናቴና የውብነሽ ከአሁን አሁን ተናግሮ ጉድ ይፈላ ይሆን በማለት
በአስጨናቂ ሐሳብ እንደሚሠቃዩ ስጋታቸው በየፊታቸው ላይ ይታወቃል፡፡ ከእኔ ጋር ማዶ ለማዶ መፋጠጡን ስለ ጠሉት ሁለቱም ወደ ማድ ቤት ወረዱ፡፡
እኔና አባቴ በጣም በመጠነኛ መግባባት ስለ ጭሰኛ' ስለ ግብር' ስለ ሲሶና እርቦ ስለ ገሚስና ከአሥር አንድ፣ እንዲሁም ስለ ሕግና ስለ እኔ የልጅነት ዓመታት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት እንደነገሩ አወራን። ከዚያ በኋላ
ግን፡ እነዚያ ለሁለት ሳምንት የተለዩት የወንጀለኛ መቅጫና የፍትሐ ብሔር ሕግ መጻሕፍት ትዝ ስላሉት «ትንሽ ሥራ አለብኝ፡ ከእናትህና ከአጎትህ ጋር ተጫወት» ብሎኝ ወደ መኝታ ቤት ገባ።
ከአባቴ ጋር ተዝናንቼ ሳወራና ስጫወት በመልሶቼም እየተማመንኩ ስመልስ የመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ አባቴ ገባ ከማለቱ እኅቴና እናቴ ተካ አሉ።
የፌሩት ጉዳይ ባለመነገሩ የሁለቱም ፊት ፈገግታ አጋተ። ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አባቴ እንደገና ተመልሶ መጣ። ኖር ብለን ተቀበልነው። እምብዛም
ሳይጠጋ ቆም አለና እነዚያን በዕድሜና በክርክር ጽሑፍ ንባብ የተዳከሙ ዐይኖቹን በግራ እጅ ጣቶች እያሻሸ ሳልነግርህ እንዳትሄድ ብዬ ነው የተመለስኩት ዘንድሮስ በጣም ጎብዘሃል አሉ፡፡ መቼ እንደሆነ አላውቅም፡ አንድ ወዳጂ ሰዉ ጋር መንገድ ላይ አየሁት ብሉ ነገረኝ። አዎ ምንም ይሁን ምን እያደር ልብ
ሲገዙ ነው የሚታወቀው» አለና የቤቱን ግድግዳ ባይኑ ዞረው፡፡ የእናቴን የየውብነሽ ልብ በፍርሃት ተበዝብዞ ፊታቸው ድንጋጢ በሚያሯሩጠው ደም ጢም
ኣለ።
ከተቀመጥኩበት ተነሥቼ «ምን ነገሩሁ? ምን አሉህ?» አልኩና የሰማውን ለመስማት ጓጓሁ። «እሱስ ይሁን፡ እንዲያው እስከ ዛሬ ለምን ደብቀሽኝ ብዬ ነው:: ነገ እነግርሃለሁ፡፡ አበጀህ! ጠላትም ወዳጅም ደስ አይበለው ብሎ ለመመለስ ሲጀምር «አሁኑኑ ብትነግረኝስ?» አልኩት፡፡
«ነገም እኮ ሩቅ አይደለም። ነገ ይሻላል» ብሎ ሊገባ ሲል «እኔም ብዙ ነገር እነግርሃለሁ» አልኩና እኔም ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ እናቴ በፍርሃትና በጥርጣሬ እየዋለለች «ምን ሰምቶ ይሆን? ምን ነግረውት ይሆን ጌታዬ?» አለች
ከንፈሯ ሥር በሚንደፋደፉ ቃላት።
«ነገ በአንድ ላይ እንሰማዋለን» ብዬ ሊንቀሳቀስ የነበረውን ነገር እንዳጠፋ ልጅ ኮረኮምኩት፡፡ ነገሩ ሁለት ቤት ያለው ሆነና ራቴን በልቼ ወደ ቤቴ ተመለስኩ።
የዕለቱን ወሬ ለመስማት በከፍተኛ ጉጉት የምትጠባበቀዋ የወዲያነሽ፣ ከልጅዋ ጋር ስታወራ ደረስኩ እና ከጎኗ ተቀመጥኩ፡፡ ከእኛ ራቅ ብሎ በብረት
ምድጃ ውስጥ የተንተረከከው የከሰል ፍም የቢቱን አየር አሙቆታል። በወላጆቼ ቤት ስላጋጠመኝ ነገር አንድ በአንድ ጠየቀችኝ፡፡ የየወዲያነሽ ነገር ስለሆነብኝ ደከመኝና ታከተኝ ሳልል መለስኩላት፡፡ «እኛንስ መቼ ነው የምትወስደንና እጅ
ነሥተን፤ ጫማ ስመን፤ የሚሉንን የሚሉን?» አለችና የመንፈስ ጭንቀት ስለ ተሰማት አቀረቀረች። «በክብርና በይፋ ነው ይዤሽ የምቀርበው! ይህቺ የማከብራትና የምወዳት ባለቤቴ ናት ብዬ የምናገረውና የማስረዳው እኔ ነኝ፡፡በመለማመጥና በማጎብደድ ሳይሆን አባቴ በመሆኑና ለወላጅነቱ ክብር ብቻ ብዩ ያውም ክብረ ሕሊናሽን በማይነካ ሁኔታ እጅ ትነሺ ይሆናል» ብዬ አገጫን ይዤ አበረታታኋት።
«አንተ እንዳልከ! እኔ እንዲሁ ነው የምቀባጥረው» ብላ፤ ረጋ ባለ
እረማመድ ወደ ጓዳ ገባች፡፡ በውስጧ ፍርሃት እንደልቡ ይጨፍራል፡፡ከሠራተኛይቱ ጋር ራት አቀረቡ፡፡ መብላቴን ሳልናገር ደስ ይላት ዘንድ ዝግ ብዬ በላሁ። ጋሻዬነህ እንኳ ወግ ደርሶት «በእማምዬ ሞት፡ በእኔ ሞት» እያለ ደጋግሞ አጎረሰኝ፡፡ ዕለታዊ ድርጊት የአካባቢ ቅጂ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ሰኞና ማክሰኛ ተከታታዮቹም ቀናት በየተራ አልፈው ቅዳሜ ደረሰ፡፡ሁላችንም በሐሳባችን እንደ ጸናን ሰነበትን
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ዘጠኝ ተኩል ገደማ ላይ ደርሶ ብርድ ብርድ ስላለኝ ፀሐይ ለመሞቅ ምድረ ግቢው መኻል ተቀመጥኩ በየወዲያነሽ አእምሮ ውስጥ
ያለው ጥያቄ ሳይመለስ በመሰንበቱ ሥጋቷ አልተወገደም፡፡ በአንዲት ትንሽ ነጭ ፎጣ ብርጭቆ እየወለወለች ዝግ ብላ መጣችና “አሁን ነው እንዴ የምንሄደው? እ...!» ብላ ንግግሯን በጥያቄ አንጠለጠለችው::
«አንቺና ጋሻዬነህ የምትሄዱት ሌላ ጊዜ ነው:: ቀኑን እኔና አንቺ
እንወስነዋለን፡፡ ዛሬም ሆነ ነገ የምሄደው እኔ ነኝ። ከነዚያ ከተከለከሉ መጻሕፍት አንብባ የነገረችሽን የእስረኛዋን ጓደኛሽን የምክር ቃላት አትርሺ፡ መብት
የሚገኘው በትግል ነው፡፡ ጨቋኞች በሰላምና በውዴታ መብት እይሰጡም ብላ
ነግራኛለች አላልሽም? እኔና አንቺም» ብዬ ዝም አልኳት። ከጀመርኩት አርእስት ውጪ «አዎ እውነትህን ነው: ከመንገድ ሲገቡ ያላሰቡትን ያልሰሙትን ነገር ተናግሮ ክፉም ደግም መስማትና መናገር ለእርሳቸውም ሆነ
ለእኛ ነገር ማበላሸት ነው» ብላ የብርጭቆይቱን ጥራት ለማረጋገጥ ትክ ብላ ተመለከተቻት ንግግሯን ሰምቼ ዝም ስላልኩ ወደ ቤት ገባች፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አባቴን እንኳን ደኅና” መጣህ ለማለት ወደ ወላጆቼ ቤት ገሠገሥኩ፡፡
ባለፈው ጊዜ ወላጆቼን ለመጠየቅ ስሔድ ይጨመድደኝ የነበረው
ሥጋትና ፍርሃት እንዲሁም የሕሊና ረብሻ እጅግ በጣም ተቀነሰ። እረጋገጤ ደልዳላ ከመሆኑም በላይ ቀና ብዬ ተራመድኩ፡፡ ዱሮ ደረጃውን የምወጣው አንድ
በአንድ ሲሆን ዛሬ ግን ሁለትና ሦስቱን በአንድ ጊዜ አጠቃለልኩት። ደረጃውን
ጨርሼ ፊቴን ወደ በሩ መለስ ሳደርግ የብዙ ሰዎች ድምፅ ሰማሁ፡፡ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ የነበረኝ ድፍረት ከፍ አለ። እቤቱ ውስጥ ለነበሩት ሁሉ ጎንበስ ብዬ
እጅ ነሣሁ፡፡ ከዚያም በቀጥታ ወደ አባቴ ሄድኩና እጅ ነሥቼ ጨበጥኩት።
«እንኳን ደኅና ገባህ! የሄድክበት ሁሉ ቀናህ! » አልኩና አንገቴን በትሕትና ሰበር አድርጌ ከፊቱ ገለል ብዬ ቆምኩ፡፡
እንኳን ደኅና ቆያችሁኝ አዎ ደኅና ደርሼ መጣ። ሁሉም ደህና
ቆየኝ። ክብሩ ይስፋ!ና! እዚች አጠገቤ ና አጠገቡ የነበረውን ወንበር በጣቱ አሳየኝ። እንኳን በደህና ገቡ ለማለት ያመጡትንና ሌሎችንም እንግዶች አንድ
በአንድ አየኋቸው፡፡ በሰዎች ላይ የሚታየው ፈገግታና የአቀማመጣቸው ሁናቴ
የተለያየ በመሆኑ አባቴን በተለያየ የአስተሳሰብ ደረጃ እንደሚመለከቱት ያስታውቃል። አንዳንዱ ውስጣዊ ጭንቀት አስገድዶት በግድ ፈገግ ብሏል።
ለማስደሰትና በግድ ለመደሰት ብሉ በደረቅ ፈገግታ ፊቱን ያጨማደደም አለ።የአንዳንዶቹን ፊት ደግሞ የበታችነት ስሜት ስለተጫነው ፊታቸው ከልቅሶ በኋላ የሚታይ ፊት እንጂ ለደስታ የቀረበ ገጽታ አይመስልም፡፡
ሁለትና ሦስቱን እንደ አባቴ የቅርብ ጓደኞች ስለምመለከታቸው በእነርሱ ላይ የነበረኝን ጥላቻ ለመርሳትም ሆነ ለማሻሻል ያለኝ አቅም በጣም አነስተኛ ነበር። ሕሊናዬ ዘወትር ይበቀላቸዋል፡፡ ወረቀት እያገላበጡ የሚዶልቱት ሁሉ ትውስ ሲለኝ፡ የሰውን ሕልውና አርደውና አወራርደው የሚገድሉ ይመስሉኛል።
ክርክርና ወሬ ሲጀምሩ ማንም በአጠገባቸው እንዲያልፍ ስለማይፈልጉ ዓለምን
የተንኮል ገበያ እንጂ የመልካም ምግባር አደባባይ እንድትሆን የሚያስቡ አይመስሉም፡፡ እናቴ እንኳን ደበቅ እያለች «መጡ ደግሞ እነ ጋጠው ገሽልጠው»
ትላቸው ነበር፡፡
ለእኔም እንደ እንግዶቹ ጠላ ደረሰኝ፡፡ ከዚህም ከዚያም የሚመጣውን ወሬ እየሰማሁ ጠላዬን ሁለት፣ ሦስት ጊዜ አስሞላሁ፡፡ እንግዶቹ አንድና ሁለት እየሆኑ ተራ በተራ እጅ እያነሡ ሄዱ።
እናቴና የውብነሽ ከአሁን አሁን ተናግሮ ጉድ ይፈላ ይሆን በማለት
በአስጨናቂ ሐሳብ እንደሚሠቃዩ ስጋታቸው በየፊታቸው ላይ ይታወቃል፡፡ ከእኔ ጋር ማዶ ለማዶ መፋጠጡን ስለ ጠሉት ሁለቱም ወደ ማድ ቤት ወረዱ፡፡
እኔና አባቴ በጣም በመጠነኛ መግባባት ስለ ጭሰኛ' ስለ ግብር' ስለ ሲሶና እርቦ ስለ ገሚስና ከአሥር አንድ፣ እንዲሁም ስለ ሕግና ስለ እኔ የልጅነት ዓመታት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት እንደነገሩ አወራን። ከዚያ በኋላ
ግን፡ እነዚያ ለሁለት ሳምንት የተለዩት የወንጀለኛ መቅጫና የፍትሐ ብሔር ሕግ መጻሕፍት ትዝ ስላሉት «ትንሽ ሥራ አለብኝ፡ ከእናትህና ከአጎትህ ጋር ተጫወት» ብሎኝ ወደ መኝታ ቤት ገባ።
ከአባቴ ጋር ተዝናንቼ ሳወራና ስጫወት በመልሶቼም እየተማመንኩ ስመልስ የመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ አባቴ ገባ ከማለቱ እኅቴና እናቴ ተካ አሉ።
የፌሩት ጉዳይ ባለመነገሩ የሁለቱም ፊት ፈገግታ አጋተ። ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አባቴ እንደገና ተመልሶ መጣ። ኖር ብለን ተቀበልነው። እምብዛም
ሳይጠጋ ቆም አለና እነዚያን በዕድሜና በክርክር ጽሑፍ ንባብ የተዳከሙ ዐይኖቹን በግራ እጅ ጣቶች እያሻሸ ሳልነግርህ እንዳትሄድ ብዬ ነው የተመለስኩት ዘንድሮስ በጣም ጎብዘሃል አሉ፡፡ መቼ እንደሆነ አላውቅም፡ አንድ ወዳጂ ሰዉ ጋር መንገድ ላይ አየሁት ብሉ ነገረኝ። አዎ ምንም ይሁን ምን እያደር ልብ
ሲገዙ ነው የሚታወቀው» አለና የቤቱን ግድግዳ ባይኑ ዞረው፡፡ የእናቴን የየውብነሽ ልብ በፍርሃት ተበዝብዞ ፊታቸው ድንጋጢ በሚያሯሩጠው ደም ጢም
ኣለ።
ከተቀመጥኩበት ተነሥቼ «ምን ነገሩሁ? ምን አሉህ?» አልኩና የሰማውን ለመስማት ጓጓሁ። «እሱስ ይሁን፡ እንዲያው እስከ ዛሬ ለምን ደብቀሽኝ ብዬ ነው:: ነገ እነግርሃለሁ፡፡ አበጀህ! ጠላትም ወዳጅም ደስ አይበለው ብሎ ለመመለስ ሲጀምር «አሁኑኑ ብትነግረኝስ?» አልኩት፡፡
«ነገም እኮ ሩቅ አይደለም። ነገ ይሻላል» ብሎ ሊገባ ሲል «እኔም ብዙ ነገር እነግርሃለሁ» አልኩና እኔም ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ እናቴ በፍርሃትና በጥርጣሬ እየዋለለች «ምን ሰምቶ ይሆን? ምን ነግረውት ይሆን ጌታዬ?» አለች
ከንፈሯ ሥር በሚንደፋደፉ ቃላት።
«ነገ በአንድ ላይ እንሰማዋለን» ብዬ ሊንቀሳቀስ የነበረውን ነገር እንዳጠፋ ልጅ ኮረኮምኩት፡፡ ነገሩ ሁለት ቤት ያለው ሆነና ራቴን በልቼ ወደ ቤቴ ተመለስኩ።
የዕለቱን ወሬ ለመስማት በከፍተኛ ጉጉት የምትጠባበቀዋ የወዲያነሽ፣ ከልጅዋ ጋር ስታወራ ደረስኩ እና ከጎኗ ተቀመጥኩ፡፡ ከእኛ ራቅ ብሎ በብረት
ምድጃ ውስጥ የተንተረከከው የከሰል ፍም የቢቱን አየር አሙቆታል። በወላጆቼ ቤት ስላጋጠመኝ ነገር አንድ በአንድ ጠየቀችኝ፡፡ የየወዲያነሽ ነገር ስለሆነብኝ ደከመኝና ታከተኝ ሳልል መለስኩላት፡፡ «እኛንስ መቼ ነው የምትወስደንና እጅ
ነሥተን፤ ጫማ ስመን፤ የሚሉንን የሚሉን?» አለችና የመንፈስ ጭንቀት ስለ ተሰማት አቀረቀረች። «በክብርና በይፋ ነው ይዤሽ የምቀርበው! ይህቺ የማከብራትና የምወዳት ባለቤቴ ናት ብዬ የምናገረውና የማስረዳው እኔ ነኝ፡፡በመለማመጥና በማጎብደድ ሳይሆን አባቴ በመሆኑና ለወላጅነቱ ክብር ብቻ ብዩ ያውም ክብረ ሕሊናሽን በማይነካ ሁኔታ እጅ ትነሺ ይሆናል» ብዬ አገጫን ይዤ አበረታታኋት።
«አንተ እንዳልከ! እኔ እንዲሁ ነው የምቀባጥረው» ብላ፤ ረጋ ባለ
እረማመድ ወደ ጓዳ ገባች፡፡ በውስጧ ፍርሃት እንደልቡ ይጨፍራል፡፡ከሠራተኛይቱ ጋር ራት አቀረቡ፡፡ መብላቴን ሳልናገር ደስ ይላት ዘንድ ዝግ ብዬ በላሁ። ጋሻዬነህ እንኳ ወግ ደርሶት «በእማምዬ ሞት፡ በእኔ ሞት» እያለ ደጋግሞ አጎረሰኝ፡፡ ዕለታዊ ድርጊት የአካባቢ ቅጂ ነው፡፡
👍3
#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አረ የምን አጥር መዝለል አጥር የምታዘልልና ጥቅጥቅ ባለ ጨላማ የምታስሮጥ ዘንካታ አለችኝ አልኩና እናቴና የውብነሽን አየኋቸው።ክፉኛ ደንግጠዋል።
አባቴ፡ በንቀትና በችላ ባይነት እግሮቹን ከዘረጋ በኋላ አይሄሄ
ለጉራማ ማን ብሎህ! ማን ይችልህና! ቆየት ብለህማ እንደ እስክንድር በባለ ክንፍ ፈረስ ጋልቤያለሁ ሳትል ትቀራለህ? ዛሬስ ብለህ ብለህ ይሉኝታውንም እርግፍ አድርህ ትተህዋል! ሲሉ ሰምተሃል መሰል ደግሞ አጥር የምታዘልል አለች ወግ ነው! አታደርገውም እንጂ የወንድ ልጅ ሙያ ነው። ተከሶና ተታኮሶ
ቆንጆን ነጥቆ ማምጣት በእኛ ጊዜ ቀረ፡፡ ይቺን እናትህን ስንቱ ጎበዝ ጎረምሳ የትልልቅ ሰው ልጅ ነበር የከጀላት። እኔ አባትህ ግን እሳት የላስኩ፡ እሳት የጎረስኩ ስለ ነበርኩ፡ የሚያይብኝን ሁሉ በቁሙ አጭረቀርቀው ነበር። እከሌ እኮ
ቀና ብሉ አያት፡ አነጋገራት፡ በቤቷ አጠገብ አለፈ ሲሉ የሰው እንደሆነ እማኝ በሌለበት ቦታ ጠብቄ በጆሮ ግንዱ ነበር የማጮህበት። በዚህ ዐይነት አንድ
ዙር የዝናር ጥይት ነበር የጨረስኩት። የኋላ ኋላ ግን ተንቀባርሬ፡ ኮርቼ ስሜን
አስጠርቼና አስከብሬ ወሰድኳት» አለና የተናገረውና ያስታወሰው ሁሉ እውነት መሆኑን ለማስመስከር እናቴን በኩራት አያት፡፡
«በእናንተ የወጣትነት ዕድሜ ያገለገለው ጥይትና ዛሬ በእኛ ጊዜ ያለው ጥይት ልዩነት አለው። የምናነጣጥረውና የምንተኩሰውም በልዩ ዘዴና አኳኋን ነው:: ለልዩ ድልና ለአዲስ ዓላማ ነው፡፡ የእናንተ ትግልና የኑሮ ጎዳና አንድ ቢበዛም ሁለት እንጂ ከዚያ በላይ አይወጣም፡፡ ዛሬ ላይ ቆመን ከትላንትና የተሻገሩልንን ልዩ ልዩ የሚታዩና የማይታዩ ነገሮች በመዋጋትና በመለወጥ ላይ
ነን። የትላንትናን ጥሩ ጥሩ ነገሮች ለወደፊት እያስተላለፍን መጥፎ መጥፎውን እየነቀልን ለማንጓለል ተሰናድተናል፡፡ እያንጓለልም ነው። የእኔን የኑሮ ጦርነት ድሉች ስትሰማ ትደነቃለህ። አሁን ለጊዜው መድፍና መትረየስ ያለበት እንዳይመስልህ?» ብዬ አእምሮዬ ውስጥ ካካበትኩት ሓሳብ ውስት በጭቄ
እንደቀልድ አሰማሁት።
«ጉድ ነው! ዛሬስ እዚሁ እፊቴ ቁጭ ብሎ ማይጨው ዘመትኩ ሊል ነው። ደርሶ ባለ ጦርነት መቼ የታወጀው ጦርነት ነው በል? እዚህ በያባሕር ዛፎች ውስጥ መሽጋችሁ እንዴ!» አለና ጎላ ያለ የፌዝ ሣቅ ስቆ ዝም አለ።
እኔ የማቀርብልህና የማብራራልህ አንተ እምታነበውን የነጋሪት ጋዜጣ ዐይነት ሳይሆን ሌላ ያውም ልዩ ሕዝባዊ ነጋሪት ጋዜጣ አለኝ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሕሊናዩ ጓዳ ውስጥ ያስቀመጥኩትን ዐዋጅ በይፋ አሰማሃለው። መስማት ብቻ
ሳይሆን በተጨባጭ እያየህ፣ ትዳስሳለህ!» ብዬ አእምሮውን ለማወቅ ያህል ዝም አልኩ፡፡
«እኔ አባትህ አሁንም ቢሆን ጀግና ነኝ፡፡ የምርበተበትና የምፈራ
አይምሰልህ፡፡ አንተ ዐዋጅ የምትለው የመንደሩን አሉባልታና ወሬ እንዳይሆን ይዘኸው ና። የፈለግኸውን ይዘህ ብትመጣ እያብራራሁ እሸነሽንልሃለሁ። ጦርነት በምትለው የወሬ ዘመቻ ላይ ጀብዱ ሠርተህ ከሆነም እሽልምሃለሁ። ለሞየትም ዝግጁ ነኝ» በማለት ከነትምክህቱ ተኮፈሰ በንግግራችን ወቅት አነጋገሬ ሁሉ
ፍራቻ ስላልተጠናወተው ራሴን ዛሬስ በርትተሃል፡ በዚህ አያያዝ መግፋትና መቀጠል ነው» አልኩት። አጎቴና እናቴ አፍላፍ ገጥመው የስጋት ወሬያቸውን
ይሰልቃሉ፣ እነርሱንም ስጋት ይድሳቸዋል። ወደ እኛ ዞር እንዲሉ በማለት ድምፄን ከፍ አድርጌ ትላንትና ማታ እኮ እነግርሃለሁ ብለህ የተለያየነው በቀጠሮ ነው። በትላንትና ውስጥ ሆነን ነገ የምንለው ዛሬን ነው። እዚህም
የረጂም ጊዜ ቀጠሮ መስጠት ደስ ይልሃል እንዴ?» ብዬ ዐመድና ቅንቅኗን እንደምታራግፍ ዶሮ እጆቼን ዘርግቼ ተንጠራራሁ።
ያለቦታው ያነሳሁት ሐሳብና
ቃል ራሴን መልሶ ቅር አሰኘኝ፡፡ እሱም በትዝብት ገረመመኝ፡፡ «
ይኸነዬ ጨንቆህ ነው። ቡቡ ነህ! ብኩን ነህ አላልኩህም? ወኔህ በቀላሉ ይቀልጣል፡፡ በል ልገላግልህ! ቀኛዝማች ጥበበ ሥላሴን ታውቀው የለ? እሱ ታድያ ልጅህ መኪና ገዝቷል እንዴ? ሲነዳ አየሁት፥ ብሎ ነገረኝ፡፡ ነገሩ በጣም የሚያስደንቅ ባይሆንም
ባቄላ የምታህል ልብ በመግዛትህ ደስ ስላለኝ ነው:: እጎንህም ሰው ነበር አለኝ መሰለኝ። ይኸው ነው ሌላ አይምሰልህ፡ ወይም የተውሶ መኪና ስትነዳ አይቶህ ይሆናል፡፡ ደኅና ጓደኛ ማበጀትም እኮ ቁም ነገር ነው» ብሎ ተነሣ፡፡
የተውሶ አይደለም፤ እኔው ራሴ ገዝቻለሁ» ብዩ እኔም ቆምኩ፡፡ «ደግ አድርገሃል፣ እንግዲህ ቀስ በቀስ ሰው ልትሆን ነው፡፡ በርታ! እኔ ደግሞ በበኩሌ
ያሰብኩትን በቅርቡ እነግርሃለሁ፡፡ ደግሞ ምንድነው እያልክ ስትጨነቅ እንዳትሰነብት የሌላ አይምሰልህ። ጉልቻን የመሰለ ነገር የለም፡፡ የደኅና ሰው ዘር፣
የጨዎ ልጅ ማግባትም እኮ ማንም ተመኝቶ የማያገኘው ትልቅ ማዕረግ ነው»
ብሉ ወደ መኝታ ቤት ለመግባት መንገድ ሲጀምር «በል ከእነሱ ጋር ተጫወት አደራችሁን እንቅልፌን ሳልጨርስ እንዳትቀሰቅሱኝ» ብሎ ገባ፡፡
የእኅቴና የአናቴ አንጎል ሲጨነቅበት አድሮ የዋለበት ጉዳይ በዚህ ሁኔታ በማለፉ በልባቸው እፎይ አሉ። ኣባቴ በወጣትነቱና በጐልማሳነቱ ብዙ ያየና ያሳለፈ በመሆኑ የእኔን ከቤት መውጣት እንደ አንድ ትልቅ ኃጢአትና በደል አልቆጠረውም፡፡ 'ወንድ ልጅና አንበሳ የትም ሄዶ የትም ገብቶ ማደር አለበት”
የሚለው አነጋገሩ እኔን በቸልታ የማያው ምክንያት ነበረች።
ከግማሽ ሰዓት በኋላ የባጥ የቆጡን አወራርቼ «ደኅና እደሩ» ብዩ ወጣሁ፡፡ የቤቱን ዙሪያ ቆም ብዬ ተመለከትኩት። የትዝታ ጥላ እንጂ የሕልውና አለኝታ አልሆንልህ አለኝ፡፡ ቤቴ ስገባ ጉልላትና የወዲያነሽ ፊት ለፊት
ተቀምጠው መጽሐፍ ያነብባሉ፡፡ ሰላምታ አቅርቤ ከጉልላት ጐን እንደ ተቀመጥኩ ሁለት ሰዓት ሙሉ አንተን ስጠብቅ ቆየሁ፡ ቀጠሮዬን ረሳኸው እንዴ» ብሎ
ከአንገት በላይ ኩርፈያው አሳየኝ። መለስ ብዬ ሳይ የወዲያነሽ ቆማለች፡፡ «እረ በይልኝ! ምነው ምነው የኔ እመቤት» አልኳት፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከወንበር ላይ
የምትነሣው እንደ ዱሮው በዝቅተኛነት መንፈስ ባለመሆኑ አልከፋም።
ጉልላት የት እንደ ዋልኩ ለማወቅ ከአንገት በላይ አፈጠጠብኝ። የነገሩን አቅጣጫ ቶሎ ለመቀየር በሁለት ሰዓት ውስጥ ስንት ኩባያ ሻይ አስቀዳህ? ብዬ ስለ በረዶ ተጠይቆ ስለ ድንጋይ እንደሚያስረዳ መምህር ነገሩን አምታታሁበት።
«ካልክስ አሁንም ተጥዶልኛል፡፡ ይኸኔ ፈልቷል» ብሎ የወዲያነሽን
መለስ ብሉ በእዎን በይልኝ ተመለከታት፡ በሁለቱ መካከል ያለው መግባባት ከፍ ያለ በመሆኑ እንቅስቃሴዎቹን ሁሉ እንደ እጅ ጣቶቿ ታውቃቸዋለች። የወዲያነሽ
ወዲያውኑ ብር ብላ ሄዳ ሻይ ይዛ በመመለስ አጠገቡ ቆም ብላ ትከሻውን ተመረኮዘች። የየወዲያነሽን የእርግዝና መጠን ወደ ጐን እየተመለከተ «ወንድ
ከሆነ የክርስትና አባቱ እኔ መሆን አለብኝ» አለና ከቀረበለት ሻይ ላይ ፉት አለ፡፡ «ሴት ከሆነችሳ?» አልኩት።
«ሴት ከሆነችማ ለማን ልበልህ? ለዚያች እኔና አንተ ለምናውቃት ሊ....ብሎ» በርግጠኛነት ምራቁን ዋጠ፡ የምንነጋገረው ስለ እርሷ መሆኑን በማወቅ በመጠኑ አፍራ ተቅለሰለሰች።
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...አረ የምን አጥር መዝለል አጥር የምታዘልልና ጥቅጥቅ ባለ ጨላማ የምታስሮጥ ዘንካታ አለችኝ አልኩና እናቴና የውብነሽን አየኋቸው።ክፉኛ ደንግጠዋል።
አባቴ፡ በንቀትና በችላ ባይነት እግሮቹን ከዘረጋ በኋላ አይሄሄ
ለጉራማ ማን ብሎህ! ማን ይችልህና! ቆየት ብለህማ እንደ እስክንድር በባለ ክንፍ ፈረስ ጋልቤያለሁ ሳትል ትቀራለህ? ዛሬስ ብለህ ብለህ ይሉኝታውንም እርግፍ አድርህ ትተህዋል! ሲሉ ሰምተሃል መሰል ደግሞ አጥር የምታዘልል አለች ወግ ነው! አታደርገውም እንጂ የወንድ ልጅ ሙያ ነው። ተከሶና ተታኮሶ
ቆንጆን ነጥቆ ማምጣት በእኛ ጊዜ ቀረ፡፡ ይቺን እናትህን ስንቱ ጎበዝ ጎረምሳ የትልልቅ ሰው ልጅ ነበር የከጀላት። እኔ አባትህ ግን እሳት የላስኩ፡ እሳት የጎረስኩ ስለ ነበርኩ፡ የሚያይብኝን ሁሉ በቁሙ አጭረቀርቀው ነበር። እከሌ እኮ
ቀና ብሉ አያት፡ አነጋገራት፡ በቤቷ አጠገብ አለፈ ሲሉ የሰው እንደሆነ እማኝ በሌለበት ቦታ ጠብቄ በጆሮ ግንዱ ነበር የማጮህበት። በዚህ ዐይነት አንድ
ዙር የዝናር ጥይት ነበር የጨረስኩት። የኋላ ኋላ ግን ተንቀባርሬ፡ ኮርቼ ስሜን
አስጠርቼና አስከብሬ ወሰድኳት» አለና የተናገረውና ያስታወሰው ሁሉ እውነት መሆኑን ለማስመስከር እናቴን በኩራት አያት፡፡
«በእናንተ የወጣትነት ዕድሜ ያገለገለው ጥይትና ዛሬ በእኛ ጊዜ ያለው ጥይት ልዩነት አለው። የምናነጣጥረውና የምንተኩሰውም በልዩ ዘዴና አኳኋን ነው:: ለልዩ ድልና ለአዲስ ዓላማ ነው፡፡ የእናንተ ትግልና የኑሮ ጎዳና አንድ ቢበዛም ሁለት እንጂ ከዚያ በላይ አይወጣም፡፡ ዛሬ ላይ ቆመን ከትላንትና የተሻገሩልንን ልዩ ልዩ የሚታዩና የማይታዩ ነገሮች በመዋጋትና በመለወጥ ላይ
ነን። የትላንትናን ጥሩ ጥሩ ነገሮች ለወደፊት እያስተላለፍን መጥፎ መጥፎውን እየነቀልን ለማንጓለል ተሰናድተናል፡፡ እያንጓለልም ነው። የእኔን የኑሮ ጦርነት ድሉች ስትሰማ ትደነቃለህ። አሁን ለጊዜው መድፍና መትረየስ ያለበት እንዳይመስልህ?» ብዬ አእምሮዬ ውስጥ ካካበትኩት ሓሳብ ውስት በጭቄ
እንደቀልድ አሰማሁት።
«ጉድ ነው! ዛሬስ እዚሁ እፊቴ ቁጭ ብሎ ማይጨው ዘመትኩ ሊል ነው። ደርሶ ባለ ጦርነት መቼ የታወጀው ጦርነት ነው በል? እዚህ በያባሕር ዛፎች ውስጥ መሽጋችሁ እንዴ!» አለና ጎላ ያለ የፌዝ ሣቅ ስቆ ዝም አለ።
እኔ የማቀርብልህና የማብራራልህ አንተ እምታነበውን የነጋሪት ጋዜጣ ዐይነት ሳይሆን ሌላ ያውም ልዩ ሕዝባዊ ነጋሪት ጋዜጣ አለኝ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሕሊናዩ ጓዳ ውስጥ ያስቀመጥኩትን ዐዋጅ በይፋ አሰማሃለው። መስማት ብቻ
ሳይሆን በተጨባጭ እያየህ፣ ትዳስሳለህ!» ብዬ አእምሮውን ለማወቅ ያህል ዝም አልኩ፡፡
«እኔ አባትህ አሁንም ቢሆን ጀግና ነኝ፡፡ የምርበተበትና የምፈራ
አይምሰልህ፡፡ አንተ ዐዋጅ የምትለው የመንደሩን አሉባልታና ወሬ እንዳይሆን ይዘኸው ና። የፈለግኸውን ይዘህ ብትመጣ እያብራራሁ እሸነሽንልሃለሁ። ጦርነት በምትለው የወሬ ዘመቻ ላይ ጀብዱ ሠርተህ ከሆነም እሽልምሃለሁ። ለሞየትም ዝግጁ ነኝ» በማለት ከነትምክህቱ ተኮፈሰ በንግግራችን ወቅት አነጋገሬ ሁሉ
ፍራቻ ስላልተጠናወተው ራሴን ዛሬስ በርትተሃል፡ በዚህ አያያዝ መግፋትና መቀጠል ነው» አልኩት። አጎቴና እናቴ አፍላፍ ገጥመው የስጋት ወሬያቸውን
ይሰልቃሉ፣ እነርሱንም ስጋት ይድሳቸዋል። ወደ እኛ ዞር እንዲሉ በማለት ድምፄን ከፍ አድርጌ ትላንትና ማታ እኮ እነግርሃለሁ ብለህ የተለያየነው በቀጠሮ ነው። በትላንትና ውስጥ ሆነን ነገ የምንለው ዛሬን ነው። እዚህም
የረጂም ጊዜ ቀጠሮ መስጠት ደስ ይልሃል እንዴ?» ብዬ ዐመድና ቅንቅኗን እንደምታራግፍ ዶሮ እጆቼን ዘርግቼ ተንጠራራሁ።
ያለቦታው ያነሳሁት ሐሳብና
ቃል ራሴን መልሶ ቅር አሰኘኝ፡፡ እሱም በትዝብት ገረመመኝ፡፡ «
ይኸነዬ ጨንቆህ ነው። ቡቡ ነህ! ብኩን ነህ አላልኩህም? ወኔህ በቀላሉ ይቀልጣል፡፡ በል ልገላግልህ! ቀኛዝማች ጥበበ ሥላሴን ታውቀው የለ? እሱ ታድያ ልጅህ መኪና ገዝቷል እንዴ? ሲነዳ አየሁት፥ ብሎ ነገረኝ፡፡ ነገሩ በጣም የሚያስደንቅ ባይሆንም
ባቄላ የምታህል ልብ በመግዛትህ ደስ ስላለኝ ነው:: እጎንህም ሰው ነበር አለኝ መሰለኝ። ይኸው ነው ሌላ አይምሰልህ፡ ወይም የተውሶ መኪና ስትነዳ አይቶህ ይሆናል፡፡ ደኅና ጓደኛ ማበጀትም እኮ ቁም ነገር ነው» ብሎ ተነሣ፡፡
የተውሶ አይደለም፤ እኔው ራሴ ገዝቻለሁ» ብዩ እኔም ቆምኩ፡፡ «ደግ አድርገሃል፣ እንግዲህ ቀስ በቀስ ሰው ልትሆን ነው፡፡ በርታ! እኔ ደግሞ በበኩሌ
ያሰብኩትን በቅርቡ እነግርሃለሁ፡፡ ደግሞ ምንድነው እያልክ ስትጨነቅ እንዳትሰነብት የሌላ አይምሰልህ። ጉልቻን የመሰለ ነገር የለም፡፡ የደኅና ሰው ዘር፣
የጨዎ ልጅ ማግባትም እኮ ማንም ተመኝቶ የማያገኘው ትልቅ ማዕረግ ነው»
ብሉ ወደ መኝታ ቤት ለመግባት መንገድ ሲጀምር «በል ከእነሱ ጋር ተጫወት አደራችሁን እንቅልፌን ሳልጨርስ እንዳትቀሰቅሱኝ» ብሎ ገባ፡፡
የእኅቴና የአናቴ አንጎል ሲጨነቅበት አድሮ የዋለበት ጉዳይ በዚህ ሁኔታ በማለፉ በልባቸው እፎይ አሉ። ኣባቴ በወጣትነቱና በጐልማሳነቱ ብዙ ያየና ያሳለፈ በመሆኑ የእኔን ከቤት መውጣት እንደ አንድ ትልቅ ኃጢአትና በደል አልቆጠረውም፡፡ 'ወንድ ልጅና አንበሳ የትም ሄዶ የትም ገብቶ ማደር አለበት”
የሚለው አነጋገሩ እኔን በቸልታ የማያው ምክንያት ነበረች።
ከግማሽ ሰዓት በኋላ የባጥ የቆጡን አወራርቼ «ደኅና እደሩ» ብዩ ወጣሁ፡፡ የቤቱን ዙሪያ ቆም ብዬ ተመለከትኩት። የትዝታ ጥላ እንጂ የሕልውና አለኝታ አልሆንልህ አለኝ፡፡ ቤቴ ስገባ ጉልላትና የወዲያነሽ ፊት ለፊት
ተቀምጠው መጽሐፍ ያነብባሉ፡፡ ሰላምታ አቅርቤ ከጉልላት ጐን እንደ ተቀመጥኩ ሁለት ሰዓት ሙሉ አንተን ስጠብቅ ቆየሁ፡ ቀጠሮዬን ረሳኸው እንዴ» ብሎ
ከአንገት በላይ ኩርፈያው አሳየኝ። መለስ ብዬ ሳይ የወዲያነሽ ቆማለች፡፡ «እረ በይልኝ! ምነው ምነው የኔ እመቤት» አልኳት፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከወንበር ላይ
የምትነሣው እንደ ዱሮው በዝቅተኛነት መንፈስ ባለመሆኑ አልከፋም።
ጉልላት የት እንደ ዋልኩ ለማወቅ ከአንገት በላይ አፈጠጠብኝ። የነገሩን አቅጣጫ ቶሎ ለመቀየር በሁለት ሰዓት ውስጥ ስንት ኩባያ ሻይ አስቀዳህ? ብዬ ስለ በረዶ ተጠይቆ ስለ ድንጋይ እንደሚያስረዳ መምህር ነገሩን አምታታሁበት።
«ካልክስ አሁንም ተጥዶልኛል፡፡ ይኸኔ ፈልቷል» ብሎ የወዲያነሽን
መለስ ብሉ በእዎን በይልኝ ተመለከታት፡ በሁለቱ መካከል ያለው መግባባት ከፍ ያለ በመሆኑ እንቅስቃሴዎቹን ሁሉ እንደ እጅ ጣቶቿ ታውቃቸዋለች። የወዲያነሽ
ወዲያውኑ ብር ብላ ሄዳ ሻይ ይዛ በመመለስ አጠገቡ ቆም ብላ ትከሻውን ተመረኮዘች። የየወዲያነሽን የእርግዝና መጠን ወደ ጐን እየተመለከተ «ወንድ
ከሆነ የክርስትና አባቱ እኔ መሆን አለብኝ» አለና ከቀረበለት ሻይ ላይ ፉት አለ፡፡ «ሴት ከሆነችሳ?» አልኩት።
«ሴት ከሆነችማ ለማን ልበልህ? ለዚያች እኔና አንተ ለምናውቃት ሊ....ብሎ» በርግጠኛነት ምራቁን ዋጠ፡ የምንነጋገረው ስለ እርሷ መሆኑን በማወቅ በመጠኑ አፍራ ተቅለሰለሰች።
👍4
#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ዳፈና ውስጥ ተጎልቶ እየተቆሰቆሰ የሚበራ የማገዶ ብርሃን እንደሚጠባበቅ ሰው ሕሊናዬ በተመስጦና በጉጉት የሚጠባበቀው እሑድን እንጂ
ረቡዕንና ሐሙስን አልነበረም፡፡ እያንዳንዷ ቀን በዕጥፍ እየተቀመጠለች ብታጥር
ባልጠላሁ፡፡ ያም ሆነ ይህ ረቡዕና ሐሙስ እንዲሁም ዓርብ ተራ በተራ አለፉ፡፡የሕሊናዬ ጠቅላላ ዝግጅት ለእሑድ ትንቅንቅ ክተት አለ። የትግልና የቁም ነገር
ንፁህ ምርቴን የምሰበስብበት ዕለት እሑድ በመሆኑ ያ አብሮ አደጌ ፍርሃት በቁሜ እንዳያበክተኝ በማለት ተጨማሪ የክርክርና የሙግት ሸንጎ በራሴ ውስጥ
አዘጋጀሁ፡፡
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ የሁለት እምነቶች የጦፈ ግጭት የሚደረግበት ዋዜማ ነበር፡፡ ምድረ-ግቢው መኻል ዕንጨት ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ከአባቴ
ጋር በማደርገው የአስተሳሰብ ጦርነት ላይ የሚገጥመኝ የመጨረሻ ውጤት ምን ይሆን እያልኩ ሳሰላስል እቆይና «ውጣልኝ! ውጣ! አሰዳቢ! ውርደተኛ ይዘሃት ገደል ግባ!» ብሎ የጮኸብኝ እንደሆነ ምን እመልስለታለሁ? በማለት ዝግጅቴን ለማጠናከርና ራሴን ለመፈተሽ ሀ ብዬ ነገሩን ወጠንኩ፡ ድንገት ከወንበሬ ላይ ተስፈንጥሬ ተነሣሁና ያስፈለገውን ይበል፥ ይራገም! ያውግዝ! ፍትሐ ብሔሩን
እየጠቀሰ ከሚመካበት የንብረቱ ውርስ ላይ ይንቀለኝ! ይሰርዘኝ! እኔ ግን ከወሰንኳት ሐሳቤ ላይ እንዲት ጋት እንኳን ወደኋላ አልነቃነቅም፡፡ አላፈገፍግም፡፡ወደፊት መሸከም የሚገባኝን የኃላፊነት ቀንበር መሸከም አለብኝ፡ በዚያው አንፃር
ደግሞ የተገዢነትንና የባርነትን ቀንበር መሰባበርና ማነኳኮት ይጠበቅብኛል፡፡እኔው አነጣጥሬ እኔው ቃታ መሳብ ይኖርብኛል! ስለ የወዲያነሽ ሰብአዊ እኩልነት ስለ ሁለታችን የሕሊና ነጻነት ስል የሚያጋጥመኝን ችግርና ማናቸውም ተቃውሞ ሁሉ እቋቋመዋለሁ፥ እደመስሰዋለሁ» ብዩ የአባቴን የሕሊና ምስል ፊት
ለፊት አቁሜ በቁጣ አፈጠጥኩበት ደመናው ውስጥ ድብብቆሽ ስትጫወት የቆየችው ፀሐይ የእኔን ቁጣና የሕሊና ረብሻ የፈራች ይመስል ደመና ውስጥ
ጠልቃ ቀረች፡፡ እኔም ወደ ቤት ገባሁ። ወዲያ ወዲህ ብመለከት ሰው በማጣቴ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤት ዐለፍኩ፡፡ የወዲያነሽ የቀኝ እጅዋን ተንተርሳ ዐይኗን
ለእንቅልፍ ሳይሆን ለዕረፍት እንገርባዋለች። በንጹሕ የምንጭ ውሃ ላይ የምትሯሯጥ የውሃ እናት እንደሚመለከት ልጅ አሽቆልቁዬ አየኋት። ደርባባ ዝምታዋ የተንጣለለ ውበት ወለደ። አልጋው ጠርዝ ላይ ጋደም እንዳልኩ
እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ኻያ ደቂቃ ያህል እንደ ተኛሁ ባንኜ ነቃሁ። በደመና ተሽፍና የነበረችው ፀሐይ መጥለቋን የተረዳሁት ክፍሉ ውስጥ በተተካው ድንግዝግዝ
ጨለማ ነበር። ዟ ብዩ አልጋው ላይ እንደ ተንጋለልኩ የወዲያነሽ ከያዘችው የጠርሙስ ውስጥ ውሃ እየቀነሰች ግንባሬ ላይ አንጠባጠበች።
በሐሳብ መጠመዱን አውቃ በሰበቡ አናጥባ ልትገላግለኝ ነበር፡፡ ከአልጋው ላይ ዘልዩ ትልቁ ክፍል ገባሁ፡፡ ተከትላኝ ገብታ አንድ ቦታ ላይ ቆማ እየዞረች
በምሮጥበት አቅጣጫ ሁሉ ረጨችብኝ፡፡ ሣቋ ሙዚቃዬ ነው። በናትሽ ቆይ በሞቴ ተይ! እባክሽ በሰበስኩ?» እያልኩ ክፍሉን ከአራት ጊዜ በላይ ዞርኩት።
ሰው ይመጣል ብለን ሳንጠረጥር የውብነሽ ድንገት መጥታ በመካከላችን ድንቅር
አለች።
«ኧረ በገላጋይ! ለእኔ ስትይ? ለእኔ ስትይ የዛሬን?» ብላ ጠርሙሱን
ተቀበለቻት። ከውሃው ቀነስ አድርጋ እጅዋ ላይ ስታቁር አይቼ «በቃ! አንቺ ደግሞ የምን ጭማሪ ነሽ» ብዩ ካንገት በላይ ተቆጣሁ፡፡ «ታዘብኩህ! ይኸን ያህል ታደላለህ?» ብላ እያሣቀች ተቀመጠች፡፡ ከጥቂት እንቶ ፈንቶ ወሬ በኋላ «እንግዲህ ነገ ያው ነው:: በእኔ በኩል የተለወጠና የሚለወጥ ነገር የለም» አልኳት
ምናልባት ያመጣችው አዲስ ወሬና ሐሳብ እንዳለ ለማወቅ፡፡ «እናታችን እንደሆነ ከአሁኑ መርበትበት ይዛለች፡፡ የቤቱ ዕቃ ሁሉ ያነቅፋታል። ነጋ ጠባ
ያቃዠኛል ነው የምትለው፣ እኔ እንጃላት» አለችና የትካዜዋን መጠን በወኪልነት
“ለማስረዳት የተላከች ይመስል የሚያሳዝን ባዶ ትካዜ ተከዘች። «ያለቀለት ጉዳይ ነው! ቃዠችም አለመችም አቀራረቤ አይለወጥም» በማለት ውክልናዋን እንደ ጨው አሟሟሁት። ነገሩን ቀዝቀዝ ባለ ሁኔታ የተመለከትኩት ለማስመሰል
«ይልቅስ መትተው ከማይመቱት ጋር ስለምፋጠጥ ምናልባት ተበሳጭቶ የተናደደ እንደሆነ በዚያ በከዘራ እንዳያንቆራጥጠኝና አሳሬን እንዳያስጨልጠኝ በአካባቢው ያለውን በትር ሁሉ ደብቂልኝ፡፡ ስለ ሌላው አትሥጊ» ብዬ የእሑዱን ተራ ሥጋቴን ለፍሥሐም ይሁን ለኀዘን ገለጽኩላት፡፡
እኅቴና ባለቤቴ ወሬ ሲያወሩ እኔ በዝምታ ወደ ውስጤ ሠረግሁ። በልቤ ውስጥ የተከሰከሰው የሐሳብ እቃቅማ ወጋኝ፡፡ ጋሻዬነህና ሠራተኛችን ከእኔ
አቅራቢያ ተቀምጠው ተረት ትተርትለታለች፡፡ የስድስቱም ተበሉና ያንዷ የሞኝ፤ ልጅ ብቻ ቀረ። ዝም ስለምትል ነው እንጂ ሞኝ አልነበረችም። ከዚያ በኋላ
የሰባቱንም ጡት ጠብቶ ሰባት ቀንድ አወጣ» አለችው ሁላችንም ካንገት በላይ እንቶፈንቶውን ሁሉ እያወራን ቤት ያፈራውን ተጋበዝን። የውብነሽን ለመሸኘት እንደ ወጣሁ በዚያው ወደ ጉልላት ቤት ጐራ ብዬ ስጫወት አመሽሁ። የውሳኔ ማሻሻያም ሆነ የሐሳብ ለውጥ አላደረግንም፡፡ ዝግጅቱ ተጠናቆ የሕሊና ጦርነት ክተት ታውጇል። የሚቀጥለው ተግባር ነፃነት ወይም ሞት ብቻ ነው። ነፃነት ግን ይቀድማል። ማታ የወዲያነሽን ጸጥታ እንዳልነሣ ሹልክ ብዩ ገብቼ ተቀመጥኩ።
መደበኛው አንጎሌ ብቻ ሳይሆን መላው አካሌ ሆኖ የሚያስብና
የሚያሰላስል፡ ምክንያት የሚያቀርብና የሚከራከር መሰለኝ፡፡ ሰካራም ባለቤት
በታላቅ ሥጋት እንደምትጠባበቅ ሴት ብቻዬን ተጎለትኩ። ይህን ረጂም ሌሊት ልገፋው የምችለው በንባብ ነው ብዪ ንባብ ቀጠልኩ። ደፋ ቀና እያልኩ ሁለት ሰዓት ያህል ጠረጴዛው ላይ ተኛሁ፡፡በየዕንጨቱ ስንጣቂ ጭላንጭል እየሾለካ
ሚገባው ቀዝቃዛ አየር ነቃ እንድል አስገደደኝ። ቀልቤን ሰብስቦ ያለማቋረጥ ሁለት ሰዓት ያህል ካነበብኩ በኋላ በስተምሥራቅ በኩል ያለውን መስኮት ከፍቼ
አካባቢውን ቃሁት። ጭልምልምታዉ ሙልጭ ብሉ ስላልጠራ ድፍርሱ ብርሃን
ዋና ትንቅንቅ ላይ ነበር። በጋቢዩ ውስጥ መጽሐፌን ደረቴ ላይ ለጥፌ የመስኮቱን ደፍ ተደግፌ ቆምኩ። አጥቢያ ኮከብ ልክ የቀኗ ሁለት ሰዓት ፀሐይ መዳረሻ ላይ
ደርሳ ትንተገተጋለች። ቀስ በቀስ ምሥራቃዊው አድማስ ከዳር እስከ ዳር ግምጃ ለበሰ። ከተራራው በስተጀርባ ያደባችው ፀሐይ ጮራዋን ሽቅብ ወደ ሰማይ
ሰደደችው። አሞሮችና ወፎች ከዚህም ከዚያም መብረር ጀመሩ፡፡ ከየአቅጣጫው
ሲያደነቁሩኝ ያደሩት አውራ ዶሮዎች ዐልፎ ዐልፎ መኮኮል ቀጥለዋል፡፡ ከንጋቱ ዐሥራ ሁለት ሰዓት ሞላና እሑድ ሆነ።
በማለዳው ቀዝቃዛ ጭጋግማ አየር ውስጥ የጋለ የብረት አሎሎ መስላ የምትታየዋ ፀሐይ ብቅ አለች፡፡ ደመና በማይታይበት
ሰማይ ላይ የወጣችው ጀንበር በየደቂቃው ኃይልና ግለት ትጨምር ይመስል ድምቀቷና ብርሃኗ አየለ። እንዲያ እንዲያ ስትል በባዶ ዐይን ከምትታይበት
ሁኔታ ዐልፋ ተንተግታጊ ደረጃ ላይ ደረሰች። እንደ ወህኒ ዘበኛ ከወዲያ ወዲህ በማለት ላይ እንዳለሁ የወዲያነሽ አጠገቤ መጥታ ቆመች። «እስኪ አሁን እንኳ ትንሽ ጋደም በል፤ ደግ አይደለም እኮ! በኋላ እኮ ይደነዝዝሃል! ይደብተሃል»
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ዳፈና ውስጥ ተጎልቶ እየተቆሰቆሰ የሚበራ የማገዶ ብርሃን እንደሚጠባበቅ ሰው ሕሊናዬ በተመስጦና በጉጉት የሚጠባበቀው እሑድን እንጂ
ረቡዕንና ሐሙስን አልነበረም፡፡ እያንዳንዷ ቀን በዕጥፍ እየተቀመጠለች ብታጥር
ባልጠላሁ፡፡ ያም ሆነ ይህ ረቡዕና ሐሙስ እንዲሁም ዓርብ ተራ በተራ አለፉ፡፡የሕሊናዬ ጠቅላላ ዝግጅት ለእሑድ ትንቅንቅ ክተት አለ። የትግልና የቁም ነገር
ንፁህ ምርቴን የምሰበስብበት ዕለት እሑድ በመሆኑ ያ አብሮ አደጌ ፍርሃት በቁሜ እንዳያበክተኝ በማለት ተጨማሪ የክርክርና የሙግት ሸንጎ በራሴ ውስጥ
አዘጋጀሁ፡፡
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ የሁለት እምነቶች የጦፈ ግጭት የሚደረግበት ዋዜማ ነበር፡፡ ምድረ-ግቢው መኻል ዕንጨት ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ከአባቴ
ጋር በማደርገው የአስተሳሰብ ጦርነት ላይ የሚገጥመኝ የመጨረሻ ውጤት ምን ይሆን እያልኩ ሳሰላስል እቆይና «ውጣልኝ! ውጣ! አሰዳቢ! ውርደተኛ ይዘሃት ገደል ግባ!» ብሎ የጮኸብኝ እንደሆነ ምን እመልስለታለሁ? በማለት ዝግጅቴን ለማጠናከርና ራሴን ለመፈተሽ ሀ ብዬ ነገሩን ወጠንኩ፡ ድንገት ከወንበሬ ላይ ተስፈንጥሬ ተነሣሁና ያስፈለገውን ይበል፥ ይራገም! ያውግዝ! ፍትሐ ብሔሩን
እየጠቀሰ ከሚመካበት የንብረቱ ውርስ ላይ ይንቀለኝ! ይሰርዘኝ! እኔ ግን ከወሰንኳት ሐሳቤ ላይ እንዲት ጋት እንኳን ወደኋላ አልነቃነቅም፡፡ አላፈገፍግም፡፡ወደፊት መሸከም የሚገባኝን የኃላፊነት ቀንበር መሸከም አለብኝ፡ በዚያው አንፃር
ደግሞ የተገዢነትንና የባርነትን ቀንበር መሰባበርና ማነኳኮት ይጠበቅብኛል፡፡እኔው አነጣጥሬ እኔው ቃታ መሳብ ይኖርብኛል! ስለ የወዲያነሽ ሰብአዊ እኩልነት ስለ ሁለታችን የሕሊና ነጻነት ስል የሚያጋጥመኝን ችግርና ማናቸውም ተቃውሞ ሁሉ እቋቋመዋለሁ፥ እደመስሰዋለሁ» ብዩ የአባቴን የሕሊና ምስል ፊት
ለፊት አቁሜ በቁጣ አፈጠጥኩበት ደመናው ውስጥ ድብብቆሽ ስትጫወት የቆየችው ፀሐይ የእኔን ቁጣና የሕሊና ረብሻ የፈራች ይመስል ደመና ውስጥ
ጠልቃ ቀረች፡፡ እኔም ወደ ቤት ገባሁ። ወዲያ ወዲህ ብመለከት ሰው በማጣቴ በቀጥታ ወደ መኝታ ቤት ዐለፍኩ፡፡ የወዲያነሽ የቀኝ እጅዋን ተንተርሳ ዐይኗን
ለእንቅልፍ ሳይሆን ለዕረፍት እንገርባዋለች። በንጹሕ የምንጭ ውሃ ላይ የምትሯሯጥ የውሃ እናት እንደሚመለከት ልጅ አሽቆልቁዬ አየኋት። ደርባባ ዝምታዋ የተንጣለለ ውበት ወለደ። አልጋው ጠርዝ ላይ ጋደም እንዳልኩ
እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ኻያ ደቂቃ ያህል እንደ ተኛሁ ባንኜ ነቃሁ። በደመና ተሽፍና የነበረችው ፀሐይ መጥለቋን የተረዳሁት ክፍሉ ውስጥ በተተካው ድንግዝግዝ
ጨለማ ነበር። ዟ ብዩ አልጋው ላይ እንደ ተንጋለልኩ የወዲያነሽ ከያዘችው የጠርሙስ ውስጥ ውሃ እየቀነሰች ግንባሬ ላይ አንጠባጠበች።
በሐሳብ መጠመዱን አውቃ በሰበቡ አናጥባ ልትገላግለኝ ነበር፡፡ ከአልጋው ላይ ዘልዩ ትልቁ ክፍል ገባሁ፡፡ ተከትላኝ ገብታ አንድ ቦታ ላይ ቆማ እየዞረች
በምሮጥበት አቅጣጫ ሁሉ ረጨችብኝ፡፡ ሣቋ ሙዚቃዬ ነው። በናትሽ ቆይ በሞቴ ተይ! እባክሽ በሰበስኩ?» እያልኩ ክፍሉን ከአራት ጊዜ በላይ ዞርኩት።
ሰው ይመጣል ብለን ሳንጠረጥር የውብነሽ ድንገት መጥታ በመካከላችን ድንቅር
አለች።
«ኧረ በገላጋይ! ለእኔ ስትይ? ለእኔ ስትይ የዛሬን?» ብላ ጠርሙሱን
ተቀበለቻት። ከውሃው ቀነስ አድርጋ እጅዋ ላይ ስታቁር አይቼ «በቃ! አንቺ ደግሞ የምን ጭማሪ ነሽ» ብዩ ካንገት በላይ ተቆጣሁ፡፡ «ታዘብኩህ! ይኸን ያህል ታደላለህ?» ብላ እያሣቀች ተቀመጠች፡፡ ከጥቂት እንቶ ፈንቶ ወሬ በኋላ «እንግዲህ ነገ ያው ነው:: በእኔ በኩል የተለወጠና የሚለወጥ ነገር የለም» አልኳት
ምናልባት ያመጣችው አዲስ ወሬና ሐሳብ እንዳለ ለማወቅ፡፡ «እናታችን እንደሆነ ከአሁኑ መርበትበት ይዛለች፡፡ የቤቱ ዕቃ ሁሉ ያነቅፋታል። ነጋ ጠባ
ያቃዠኛል ነው የምትለው፣ እኔ እንጃላት» አለችና የትካዜዋን መጠን በወኪልነት
“ለማስረዳት የተላከች ይመስል የሚያሳዝን ባዶ ትካዜ ተከዘች። «ያለቀለት ጉዳይ ነው! ቃዠችም አለመችም አቀራረቤ አይለወጥም» በማለት ውክልናዋን እንደ ጨው አሟሟሁት። ነገሩን ቀዝቀዝ ባለ ሁኔታ የተመለከትኩት ለማስመሰል
«ይልቅስ መትተው ከማይመቱት ጋር ስለምፋጠጥ ምናልባት ተበሳጭቶ የተናደደ እንደሆነ በዚያ በከዘራ እንዳያንቆራጥጠኝና አሳሬን እንዳያስጨልጠኝ በአካባቢው ያለውን በትር ሁሉ ደብቂልኝ፡፡ ስለ ሌላው አትሥጊ» ብዬ የእሑዱን ተራ ሥጋቴን ለፍሥሐም ይሁን ለኀዘን ገለጽኩላት፡፡
እኅቴና ባለቤቴ ወሬ ሲያወሩ እኔ በዝምታ ወደ ውስጤ ሠረግሁ። በልቤ ውስጥ የተከሰከሰው የሐሳብ እቃቅማ ወጋኝ፡፡ ጋሻዬነህና ሠራተኛችን ከእኔ
አቅራቢያ ተቀምጠው ተረት ትተርትለታለች፡፡ የስድስቱም ተበሉና ያንዷ የሞኝ፤ ልጅ ብቻ ቀረ። ዝም ስለምትል ነው እንጂ ሞኝ አልነበረችም። ከዚያ በኋላ
የሰባቱንም ጡት ጠብቶ ሰባት ቀንድ አወጣ» አለችው ሁላችንም ካንገት በላይ እንቶፈንቶውን ሁሉ እያወራን ቤት ያፈራውን ተጋበዝን። የውብነሽን ለመሸኘት እንደ ወጣሁ በዚያው ወደ ጉልላት ቤት ጐራ ብዬ ስጫወት አመሽሁ። የውሳኔ ማሻሻያም ሆነ የሐሳብ ለውጥ አላደረግንም፡፡ ዝግጅቱ ተጠናቆ የሕሊና ጦርነት ክተት ታውጇል። የሚቀጥለው ተግባር ነፃነት ወይም ሞት ብቻ ነው። ነፃነት ግን ይቀድማል። ማታ የወዲያነሽን ጸጥታ እንዳልነሣ ሹልክ ብዩ ገብቼ ተቀመጥኩ።
መደበኛው አንጎሌ ብቻ ሳይሆን መላው አካሌ ሆኖ የሚያስብና
የሚያሰላስል፡ ምክንያት የሚያቀርብና የሚከራከር መሰለኝ፡፡ ሰካራም ባለቤት
በታላቅ ሥጋት እንደምትጠባበቅ ሴት ብቻዬን ተጎለትኩ። ይህን ረጂም ሌሊት ልገፋው የምችለው በንባብ ነው ብዪ ንባብ ቀጠልኩ። ደፋ ቀና እያልኩ ሁለት ሰዓት ያህል ጠረጴዛው ላይ ተኛሁ፡፡በየዕንጨቱ ስንጣቂ ጭላንጭል እየሾለካ
ሚገባው ቀዝቃዛ አየር ነቃ እንድል አስገደደኝ። ቀልቤን ሰብስቦ ያለማቋረጥ ሁለት ሰዓት ያህል ካነበብኩ በኋላ በስተምሥራቅ በኩል ያለውን መስኮት ከፍቼ
አካባቢውን ቃሁት። ጭልምልምታዉ ሙልጭ ብሉ ስላልጠራ ድፍርሱ ብርሃን
ዋና ትንቅንቅ ላይ ነበር። በጋቢዩ ውስጥ መጽሐፌን ደረቴ ላይ ለጥፌ የመስኮቱን ደፍ ተደግፌ ቆምኩ። አጥቢያ ኮከብ ልክ የቀኗ ሁለት ሰዓት ፀሐይ መዳረሻ ላይ
ደርሳ ትንተገተጋለች። ቀስ በቀስ ምሥራቃዊው አድማስ ከዳር እስከ ዳር ግምጃ ለበሰ። ከተራራው በስተጀርባ ያደባችው ፀሐይ ጮራዋን ሽቅብ ወደ ሰማይ
ሰደደችው። አሞሮችና ወፎች ከዚህም ከዚያም መብረር ጀመሩ፡፡ ከየአቅጣጫው
ሲያደነቁሩኝ ያደሩት አውራ ዶሮዎች ዐልፎ ዐልፎ መኮኮል ቀጥለዋል፡፡ ከንጋቱ ዐሥራ ሁለት ሰዓት ሞላና እሑድ ሆነ።
በማለዳው ቀዝቃዛ ጭጋግማ አየር ውስጥ የጋለ የብረት አሎሎ መስላ የምትታየዋ ፀሐይ ብቅ አለች፡፡ ደመና በማይታይበት
ሰማይ ላይ የወጣችው ጀንበር በየደቂቃው ኃይልና ግለት ትጨምር ይመስል ድምቀቷና ብርሃኗ አየለ። እንዲያ እንዲያ ስትል በባዶ ዐይን ከምትታይበት
ሁኔታ ዐልፋ ተንተግታጊ ደረጃ ላይ ደረሰች። እንደ ወህኒ ዘበኛ ከወዲያ ወዲህ በማለት ላይ እንዳለሁ የወዲያነሽ አጠገቤ መጥታ ቆመች። «እስኪ አሁን እንኳ ትንሽ ጋደም በል፤ ደግ አይደለም እኮ! በኋላ እኮ ይደነዝዝሃል! ይደብተሃል»
👍4🤔1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስለ ከዘራዎቹ ቀደም በለን ተነጋግረን ስለነበር ንቅንቄ አላለችም።
እናቴ በቅምጧ ውብነሽ በቁሟ ተንዘፈዘፉ። «አእምሮህ ብዙ ነገር
ይቋጥራል፥ በደንብ ታውቃታለህም ታስታውሳታለህም የጊዚ መርዘም ትዝታን ያመነምናታል እንጂ ፈጽሞ አይገድላትም፡፡ የዚህ ልጅ እናት የወዲያነሽ አሽናፊ ትባላለች። ባልተስተካከለና ባልተሟላ የፍቅር ሕይወት ውስጥ የተሠቃየችውና
የተንገላታችው የወዲያነሽና እኔ የተገናኘነው እዚህ ቤት ውስጥ ነው:: ሌላውን ሰፊ ሐተታና ዝብዝብ እንተወውና ከእኔ እንዳረገዘች ከዚህ ቤት ተባረረች። አነሆ እኔና እርሷ ከተፋቀርን ከስምንት ዓመታት በላይ ሆኗል» ብዬ ዝም ስል «ቀጥል! ተርክ!» ብሎ አንባረቀ፡፡
«ካንተ ቀደም ብለው ይህ ልጅ ልጂ መሆኑን የሰሙት የነባር
ምስጢሩንም ሥረ መሠረት የሚያውቁት እናቴና አጎቴ ናቸው። በከንቱ ልማዳዊ እምነት ታፍኜ ይህን መልካሙንና አስፈላጊውን ጉዳይ እንደ ነውር ቆጥሬ
ትክከለኛ የነበረውንና ያልነበረውንም ድርጊቴን አምቄው ኖሬያለሁ፡፡ አሁን ግን እውነት ራሷ ለመሰማትና ይፋ ለመውጣት በውስጤ በመብላላቷና በመብሰሷ እነሆ ይኸው አሁን በማስረዳት ላይ ነኝ፡፡ ይህ ልጅ የተረገዘው እዚህ ቤት ውስጥ
ነበር፡፡ ስለ አስተዳደጉ ግን ደረጃ በደረጃ እነግርሃለሁ:: ቆሞ ለመሔድ መዳህ ያስፈልጋል» ብዬ ንግግሬን እልባት ሳላደርግበት፥
«የት ነበር የተረዝው?» ብሎ መልሴን ለመስማት በሙሉ ስሜት
አሰፈሰፈ፡፡
«ደግሜ ላረጋግጥልሀ፤ እዚሁ ቤት ውስጥ!» ብዬ ወዲያውኑ ስለ መለስኩለት አጠገቡ የነበረውን አየር በፊቱ ስፋት ልክ ገፍቶ ወደ እናቴ ዞረ።
«የሚለውን ሰማሽ? ጉድሽ ተዘከዘከ! እውነት ከሆነ እውነት ነው በይ! ከዚህ ከዝብርቅርቅ ነገር ገላግይኝ፡ እዚህ ቤት ነገር አለ፡፡ ይኸ ዝም ዝም አያዛልቅም! ማን ነች በእርግዝናዋ ጊዜ ከዚህ ቤት የተባረረች? አውጡ! ተናገሩ!» ብሎ ቤቱን በቁጣ አናጋው::
የውብነሽ ውስጥ ውስጡን ከተጫናት ሐሳብ በድንጋጤ ባነነች፡፡ ፍርሃት አፈፍ አደረጋትና ጥቂት ወደ ኋላ አፈገፈገች።
እናቴ ጻእረ ሞት የተናነቀው ሰው መሰለች፡፡
የእኔ ሕሊና እያደር ሰላ፡፡ «እኔው ልናገር! እኔው ላስረዳ!» ብዬ
በሰፊው ለመናገር ወጠን ሳደርግ «በቃህ! ማን ጠየቀህ! ከልኩ የተረፈ ምላስ አላቸው፡፡ የእነርሱ መንታ ምላስ ምን ሆነና? ሾል ሾል አበዛህ! ከልኩ አለፈ!»
ብሎ ኩም አደረገኝ፡፡ የእናቴ ከንፈሮች በትንቅንቅ አንደሚከፈት አሮጌ የብረት በር ቀስ ብለው ከተላቀቀ በኋላ በፍርሃት የተስረቀረቁ ቃላት ማሰማት ጀመረች።
«ነገር ወዲያ ወዲህ ሆኖ አስቸግሮኝ ነው እንጂ የሱ ልጅ መሆኑን ካወቅሁ ይኸው ሁለት ሳምንት ሆነኝ፡፡ ልጁ ነው፡፡ ያቺ ያነዬ እዚህ ቤት ትሠራ
የነበረችው ሠራተኛችን እኛ ሳናውቅና ሳንሰማ ለካ ውስጥ ውስጡን» ብላ ተይው በቃሽ! አርደሽኛል! ገድለሽኛል! በቁሜ
ቀብረሽኛል!» ብሎ ከንፈሩን ነክሶ አቀረቀረ።
«ታዲያ ኑራ ኑራ የስንት ወር ነው ወንድሜ... ነፈሰ ጡር ከሆነችና ሆዷ ከለየ በኋላ ከጌታነህ ማርገዟን ቤት ዘግተን አስለፍልፈን ሰማን» ብላ ተነሣች።
ቀስ ብዬ ጋሻዬነህን በእጄ ጠቀስኩትና አጠገቤ መጥቶ ቆመ፡፡ «እግዚኦ የሰው ልብ! አንቺ አረመኔ! አንቺ ጨካኝ! ለምን
አልነገርሽኝም? ለምን ደበቅሽኝ? አንቺማ አልሠራም አልታዘዝም” ብላ በመጥገቧ አባረርኳት ነበር ያልሽኝ፡፡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይይልሽ! » ብሎ በደም ፍላት
ራሱን ነቀነቀ። የተለኮሰውን የትግል ችቦ አጥብቄ ያዝኩት፡፡ የእናቴና የየውብነሽ ሁኔታ በመጠኑ ስሳሳዘነኝ ምንም እንኳ እናቴ የምታምንበትን ሁሉ
የማላምንበትና የማልመራበት ቢሆንም የራሷንና የቤተሰባችንን የኖረ ክብር ስምና ዝና ለመጠበቅ ከፍተኛ ፍላጎት ስላላት በእርሷ ኣስተሳሰብ ማናቸውም
የቤተሰባችን ሰው ተልከስክሶ እንዲገኝ አትፈልግም፡፡ እኔ ግን አሁንም በግልጽ ልናገር! በሰዉ ልጅ እኩልነት ላይ ያላችሁን ፍፁም የተሳሳተ እምነት አላምንበትም! የእናቴንና የቤተሰቤን ፍላጎት ተጋፍቼና ጥሼ ማድረግ
'የማይገባኝን' ነገር ሁኔታው በማይፈቅድልኝና በማይደግፈኝ አካባቢ በመፈጸሜ ስሕተተኛ ነህ እባል ይሆናል፡፡ እኔ ግን አይደለሁም፡፡ የማላምንበትን ሁሉ
አልቀበልም፡፡ ተገዢነቷ ምክንያት ሆኖ ላደረስኩባት በደል በሕግና በሕሊና ችሎት ተጠያቂው እኔ ነኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን እምነታችሁን ስለማላምንበትና ጨቋኝና ረጋጭ የሆነ ልማድና እምነትንም ስለማልቀበል ወንጀለኛ አይደለሁም ብዬ በመጠኑ ጊዜያዊ የመላቀቂያ ድጋፍ ሰጠኋቸው።» አባቴ ዐይኑን በርበሬ አስመስሎና ግንባሩን አኮፋትሮ «ያም ሆነ ይህ እስካሁን ድረስ የለፈለፍከው ምንም የሚጨበጥ ቁም ነገር የለበትም» ብሎ ጉልበቱን በቡጢ ደወለው።
«አዎ ከአንተ እምነት ውጪ የሆነ
በመሆኑ በቀላሉ አይጨበጥልሀም፡፡ ልብ ብለህ ስማኝ! ማንኛውም ጤነኛ ሰው በተለይም በወጣትነቱ ጊዜ ሥጋዊ ፍላጎትና ፍቅር ባንድ ላይ ተጣምረው እንደሚይዙትና
እንደሚያጠቁት የታወቀ ነው፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሕግ ጊዜውን ጠብቆ ደርሶኛል።ያን ጊዜ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃዋን ሳይሆን ወበቷን እድንቄና ከፈቃዱም
እንደማትወጣ ተማምኜ አግባባኋት፡፡ በሁኔታዎች የተከበበ ውስጣዊ ግዴታ ባማናትም ፍቅራዊ ግፊትና ውዴታም ነበራት» ብዩ ሐሳቡን ለማወቅ ዝም አልኩ፡፡
«ለምኑ ብላችሁ ነው፣ አሁን የምትጨቃጨቁት እኮ እንዲያው ነው፡፡ምነው አንተ ዝም ብትል ልጄ? አባትህም ሲሆን ይኸው ይኸን ሰሞን ጤና አላገኘም፡፡ ያመከረኛ የደም ብዛቱ እየተነሣ ቁም ስቅሉን ያሳየዋል፡፡ ምነው
የሚልህን ብትሰማ፡ ምነው እንደ ዱሮህ ይሁን ይሁን” ብትለው::»
በንግግሬ የተደሰተ ይመስል «ቀጥል፤ አብራራልኝ! አሁን ልንገናኝ ነው!» ብሎ እንድቀጥል አዘዘ። አሳርፍ እንደ ተባለ ወታደር እጅ እግሬን አፍታትቼ ተዝናናሁ፡፡
«የእኔና የእርሷ የጋራ ሥጋዊ ፍላጎት ውጤት በማሕፀኗ ውስጥ
እርግዝናን አስከተለ፡፡ ከዚያ በኋላ ነበር እናቴ ያን በአእምሮዎ ውስጥ ተዳፍኖ የኖረውን እምነቷን ይዛ በመነሣት የትውልዳችንን ክብርና ዝና ጨዋነትና ትልቅነት አስከብራለሁ በማለት በእርግዝናዋ ጊዜ ያባረረቻት። ያም ሆነ ይህ ሲወርድ ሲዋረድ መጥቶ በወረሰችው የተሳሳተ እምነት ተገድዳ የፈጸመችው
ስሕተት በመሆኑ እርሷ ብቻዋን በደለኛ አይደለችም፡፡ የስሕተቱ ቅርንጫፍ ሳይሆን ሥርና ምንጩን መቁረጥና መድፈን ያስፈልጋል፡፡ አንድን ሰው ብቻ መወንጀል ግን ከበሽታ ጠንቆች መካከል አንዷን ብቻ እንደ መግደል ይቆጠራል፡፡
ለወዲያነሽ ያለኝ ፍቅራዊ ታማኝነት ምንጊዜም ቢሆን የማይቀነስና በማንም የተቃውሞ አስተያየት የማይሻር ነው ! » አልኩና በዕለቱ ከሚፈፀመው ጉዳይ ውስጥ አብዛኛውን በድፍረትና በጥንቃቄ አጋመስኩት።
የአባቴ ንዴት ናረ፡፡ ወደ እናቴ ዞር ብሉ «ኧረ ይቺ የወዲያነሽ
የሚላትና እንዲህ የምታስወተውተው ማን ነች? የመቼዋ ነች? እስኪ ደኅና
አደርግሽ ንገረኝ? ምን ይለጉምሻል» አለ። እናቴ በፍርሃት ወለል ወለሉን እያየች «ያነዬ ነው ቆይቷል አንዲት ጠይም መልከ ቀና እዚህ እኛ ጋ አልነበረችም እንዴ? አንተ እንኳ ረጋ ያለች
ደርባባ ነች” ብለህ አመስግነሃት አልነበረም እንዴ? እሷን ነዋ የሚልህ። ከሷ ጋር ነው ይኸ ሁሉ» ብላ ወደ ዝምታዋ ተመለሰች። የአባቴ ዐይኖች ተውዘግዝገው
ጋሻዬነህ ላይ ተተከሉ። «እረግ! እረግ! እረግ! ተይው ተይው! አገኘኋት! ይኸ ልጅ የተወለደው ከእርሷ ነው ማለት ነው?» ብሎ ከሁላችንም መልስ ጠበቀ።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስለ ከዘራዎቹ ቀደም በለን ተነጋግረን ስለነበር ንቅንቄ አላለችም።
እናቴ በቅምጧ ውብነሽ በቁሟ ተንዘፈዘፉ። «አእምሮህ ብዙ ነገር
ይቋጥራል፥ በደንብ ታውቃታለህም ታስታውሳታለህም የጊዚ መርዘም ትዝታን ያመነምናታል እንጂ ፈጽሞ አይገድላትም፡፡ የዚህ ልጅ እናት የወዲያነሽ አሽናፊ ትባላለች። ባልተስተካከለና ባልተሟላ የፍቅር ሕይወት ውስጥ የተሠቃየችውና
የተንገላታችው የወዲያነሽና እኔ የተገናኘነው እዚህ ቤት ውስጥ ነው:: ሌላውን ሰፊ ሐተታና ዝብዝብ እንተወውና ከእኔ እንዳረገዘች ከዚህ ቤት ተባረረች። አነሆ እኔና እርሷ ከተፋቀርን ከስምንት ዓመታት በላይ ሆኗል» ብዬ ዝም ስል «ቀጥል! ተርክ!» ብሎ አንባረቀ፡፡
«ካንተ ቀደም ብለው ይህ ልጅ ልጂ መሆኑን የሰሙት የነባር
ምስጢሩንም ሥረ መሠረት የሚያውቁት እናቴና አጎቴ ናቸው። በከንቱ ልማዳዊ እምነት ታፍኜ ይህን መልካሙንና አስፈላጊውን ጉዳይ እንደ ነውር ቆጥሬ
ትክከለኛ የነበረውንና ያልነበረውንም ድርጊቴን አምቄው ኖሬያለሁ፡፡ አሁን ግን እውነት ራሷ ለመሰማትና ይፋ ለመውጣት በውስጤ በመብላላቷና በመብሰሷ እነሆ ይኸው አሁን በማስረዳት ላይ ነኝ፡፡ ይህ ልጅ የተረገዘው እዚህ ቤት ውስጥ
ነበር፡፡ ስለ አስተዳደጉ ግን ደረጃ በደረጃ እነግርሃለሁ:: ቆሞ ለመሔድ መዳህ ያስፈልጋል» ብዬ ንግግሬን እልባት ሳላደርግበት፥
«የት ነበር የተረዝው?» ብሎ መልሴን ለመስማት በሙሉ ስሜት
አሰፈሰፈ፡፡
«ደግሜ ላረጋግጥልሀ፤ እዚሁ ቤት ውስጥ!» ብዬ ወዲያውኑ ስለ መለስኩለት አጠገቡ የነበረውን አየር በፊቱ ስፋት ልክ ገፍቶ ወደ እናቴ ዞረ።
«የሚለውን ሰማሽ? ጉድሽ ተዘከዘከ! እውነት ከሆነ እውነት ነው በይ! ከዚህ ከዝብርቅርቅ ነገር ገላግይኝ፡ እዚህ ቤት ነገር አለ፡፡ ይኸ ዝም ዝም አያዛልቅም! ማን ነች በእርግዝናዋ ጊዜ ከዚህ ቤት የተባረረች? አውጡ! ተናገሩ!» ብሎ ቤቱን በቁጣ አናጋው::
የውብነሽ ውስጥ ውስጡን ከተጫናት ሐሳብ በድንጋጤ ባነነች፡፡ ፍርሃት አፈፍ አደረጋትና ጥቂት ወደ ኋላ አፈገፈገች።
እናቴ ጻእረ ሞት የተናነቀው ሰው መሰለች፡፡
የእኔ ሕሊና እያደር ሰላ፡፡ «እኔው ልናገር! እኔው ላስረዳ!» ብዬ
በሰፊው ለመናገር ወጠን ሳደርግ «በቃህ! ማን ጠየቀህ! ከልኩ የተረፈ ምላስ አላቸው፡፡ የእነርሱ መንታ ምላስ ምን ሆነና? ሾል ሾል አበዛህ! ከልኩ አለፈ!»
ብሎ ኩም አደረገኝ፡፡ የእናቴ ከንፈሮች በትንቅንቅ አንደሚከፈት አሮጌ የብረት በር ቀስ ብለው ከተላቀቀ በኋላ በፍርሃት የተስረቀረቁ ቃላት ማሰማት ጀመረች።
«ነገር ወዲያ ወዲህ ሆኖ አስቸግሮኝ ነው እንጂ የሱ ልጅ መሆኑን ካወቅሁ ይኸው ሁለት ሳምንት ሆነኝ፡፡ ልጁ ነው፡፡ ያቺ ያነዬ እዚህ ቤት ትሠራ
የነበረችው ሠራተኛችን እኛ ሳናውቅና ሳንሰማ ለካ ውስጥ ውስጡን» ብላ ተይው በቃሽ! አርደሽኛል! ገድለሽኛል! በቁሜ
ቀብረሽኛል!» ብሎ ከንፈሩን ነክሶ አቀረቀረ።
«ታዲያ ኑራ ኑራ የስንት ወር ነው ወንድሜ... ነፈሰ ጡር ከሆነችና ሆዷ ከለየ በኋላ ከጌታነህ ማርገዟን ቤት ዘግተን አስለፍልፈን ሰማን» ብላ ተነሣች።
ቀስ ብዬ ጋሻዬነህን በእጄ ጠቀስኩትና አጠገቤ መጥቶ ቆመ፡፡ «እግዚኦ የሰው ልብ! አንቺ አረመኔ! አንቺ ጨካኝ! ለምን
አልነገርሽኝም? ለምን ደበቅሽኝ? አንቺማ አልሠራም አልታዘዝም” ብላ በመጥገቧ አባረርኳት ነበር ያልሽኝ፡፡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይይልሽ! » ብሎ በደም ፍላት
ራሱን ነቀነቀ። የተለኮሰውን የትግል ችቦ አጥብቄ ያዝኩት፡፡ የእናቴና የየውብነሽ ሁኔታ በመጠኑ ስሳሳዘነኝ ምንም እንኳ እናቴ የምታምንበትን ሁሉ
የማላምንበትና የማልመራበት ቢሆንም የራሷንና የቤተሰባችንን የኖረ ክብር ስምና ዝና ለመጠበቅ ከፍተኛ ፍላጎት ስላላት በእርሷ ኣስተሳሰብ ማናቸውም
የቤተሰባችን ሰው ተልከስክሶ እንዲገኝ አትፈልግም፡፡ እኔ ግን አሁንም በግልጽ ልናገር! በሰዉ ልጅ እኩልነት ላይ ያላችሁን ፍፁም የተሳሳተ እምነት አላምንበትም! የእናቴንና የቤተሰቤን ፍላጎት ተጋፍቼና ጥሼ ማድረግ
'የማይገባኝን' ነገር ሁኔታው በማይፈቅድልኝና በማይደግፈኝ አካባቢ በመፈጸሜ ስሕተተኛ ነህ እባል ይሆናል፡፡ እኔ ግን አይደለሁም፡፡ የማላምንበትን ሁሉ
አልቀበልም፡፡ ተገዢነቷ ምክንያት ሆኖ ላደረስኩባት በደል በሕግና በሕሊና ችሎት ተጠያቂው እኔ ነኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን እምነታችሁን ስለማላምንበትና ጨቋኝና ረጋጭ የሆነ ልማድና እምነትንም ስለማልቀበል ወንጀለኛ አይደለሁም ብዬ በመጠኑ ጊዜያዊ የመላቀቂያ ድጋፍ ሰጠኋቸው።» አባቴ ዐይኑን በርበሬ አስመስሎና ግንባሩን አኮፋትሮ «ያም ሆነ ይህ እስካሁን ድረስ የለፈለፍከው ምንም የሚጨበጥ ቁም ነገር የለበትም» ብሎ ጉልበቱን በቡጢ ደወለው።
«አዎ ከአንተ እምነት ውጪ የሆነ
በመሆኑ በቀላሉ አይጨበጥልሀም፡፡ ልብ ብለህ ስማኝ! ማንኛውም ጤነኛ ሰው በተለይም በወጣትነቱ ጊዜ ሥጋዊ ፍላጎትና ፍቅር ባንድ ላይ ተጣምረው እንደሚይዙትና
እንደሚያጠቁት የታወቀ ነው፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሕግ ጊዜውን ጠብቆ ደርሶኛል።ያን ጊዜ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃዋን ሳይሆን ወበቷን እድንቄና ከፈቃዱም
እንደማትወጣ ተማምኜ አግባባኋት፡፡ በሁኔታዎች የተከበበ ውስጣዊ ግዴታ ባማናትም ፍቅራዊ ግፊትና ውዴታም ነበራት» ብዩ ሐሳቡን ለማወቅ ዝም አልኩ፡፡
«ለምኑ ብላችሁ ነው፣ አሁን የምትጨቃጨቁት እኮ እንዲያው ነው፡፡ምነው አንተ ዝም ብትል ልጄ? አባትህም ሲሆን ይኸው ይኸን ሰሞን ጤና አላገኘም፡፡ ያመከረኛ የደም ብዛቱ እየተነሣ ቁም ስቅሉን ያሳየዋል፡፡ ምነው
የሚልህን ብትሰማ፡ ምነው እንደ ዱሮህ ይሁን ይሁን” ብትለው::»
በንግግሬ የተደሰተ ይመስል «ቀጥል፤ አብራራልኝ! አሁን ልንገናኝ ነው!» ብሎ እንድቀጥል አዘዘ። አሳርፍ እንደ ተባለ ወታደር እጅ እግሬን አፍታትቼ ተዝናናሁ፡፡
«የእኔና የእርሷ የጋራ ሥጋዊ ፍላጎት ውጤት በማሕፀኗ ውስጥ
እርግዝናን አስከተለ፡፡ ከዚያ በኋላ ነበር እናቴ ያን በአእምሮዎ ውስጥ ተዳፍኖ የኖረውን እምነቷን ይዛ በመነሣት የትውልዳችንን ክብርና ዝና ጨዋነትና ትልቅነት አስከብራለሁ በማለት በእርግዝናዋ ጊዜ ያባረረቻት። ያም ሆነ ይህ ሲወርድ ሲዋረድ መጥቶ በወረሰችው የተሳሳተ እምነት ተገድዳ የፈጸመችው
ስሕተት በመሆኑ እርሷ ብቻዋን በደለኛ አይደለችም፡፡ የስሕተቱ ቅርንጫፍ ሳይሆን ሥርና ምንጩን መቁረጥና መድፈን ያስፈልጋል፡፡ አንድን ሰው ብቻ መወንጀል ግን ከበሽታ ጠንቆች መካከል አንዷን ብቻ እንደ መግደል ይቆጠራል፡፡
ለወዲያነሽ ያለኝ ፍቅራዊ ታማኝነት ምንጊዜም ቢሆን የማይቀነስና በማንም የተቃውሞ አስተያየት የማይሻር ነው ! » አልኩና በዕለቱ ከሚፈፀመው ጉዳይ ውስጥ አብዛኛውን በድፍረትና በጥንቃቄ አጋመስኩት።
የአባቴ ንዴት ናረ፡፡ ወደ እናቴ ዞር ብሉ «ኧረ ይቺ የወዲያነሽ
የሚላትና እንዲህ የምታስወተውተው ማን ነች? የመቼዋ ነች? እስኪ ደኅና
አደርግሽ ንገረኝ? ምን ይለጉምሻል» አለ። እናቴ በፍርሃት ወለል ወለሉን እያየች «ያነዬ ነው ቆይቷል አንዲት ጠይም መልከ ቀና እዚህ እኛ ጋ አልነበረችም እንዴ? አንተ እንኳ ረጋ ያለች
ደርባባ ነች” ብለህ አመስግነሃት አልነበረም እንዴ? እሷን ነዋ የሚልህ። ከሷ ጋር ነው ይኸ ሁሉ» ብላ ወደ ዝምታዋ ተመለሰች። የአባቴ ዐይኖች ተውዘግዝገው
ጋሻዬነህ ላይ ተተከሉ። «እረግ! እረግ! እረግ! ተይው ተይው! አገኘኋት! ይኸ ልጅ የተወለደው ከእርሷ ነው ማለት ነው?» ብሎ ከሁላችንም መልስ ጠበቀ።
👍5❤1
#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሶሰት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስደበኝ! ወይ መቆየት! አሁንሜ ብለህ ብለህ ስለ ሕጉ አስተያየት ሰጪና እርማት አቅራቢ ሆንክ! ስንት ሊቃውንት የደከሙበትንና ያረቀቁትን ሕግ አንተ ስላቃለልከው አይቀልም።
መንገርስ ልክ ልክህን እነግርህ ነበር፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል ይልቅ ወሬሀን ጠርቅ!".ብሎ የሚሆነውን እያሳጣው በቅምጡ ተቁነጠነጠ፡፡ ሕሊናው ጉዳዩን ቢረዳም
በፈቃደኛነት እንደማይረታ፣ በጨቋኝነት የተሞላ ሕሊናው በቀላሉ እጁን እንደማይሰጥ አወቅሁ፡፡ ቢሆንም የእኔ ሕሊናና ወኔ እየሞቀና እየጎለመሰ ሲሔድ
ያ በከንቱ ግብዝነት የተወጠረው የእርሱ ሕሊና ግን ቁልቁል ሲሟሽሽ ታየኝ።
በዚሀ ልጅ እናት ላይ..» በማለት እንደገና ቀጠልኩ፡፡ «በከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የመኻል ዳኛ ሆነህ አምስት ዓመት እስራት ፊርደሀባት ነበር፡፡ በሕይወቷ ውስጥ አምስት ዓመት ብቻ ሳይሆን የሕይወቷ ብዙ
ክፍል እንዲበላሽና እንዲሰናከል ተደርጓል። ወደ ዋናው ፍሬ ነገር ልመለስና በሕግና በእውነት» ስም በተቋቋሙት ፍርድ ቤቶቻችሁ ወንጀለኛ እያላችሁ ከምትፈርዱባቸው ንጹሐን ሰዎች ይልቅ በእናንተ እጅግ ጉልህ በሆነ ጥፋትና በሚጨበጥ ኃጢኣት ወንጀለኛ በሆናችሁት ሰው በላ ሰዎች የተሞላ ነው:: ወደ ልጄ ጉዳይ ልመለስና፣ ይህ ልጅ በዕጓለ ማውታ፣ እናቱ ወህኒ ቤት ውስጥ እየማቀቀች ሳይተያዩና ሳይገናኙ በጠቅላላው አምስት ዓመት ተለያይተው ቆይተዋል፡፡ እዚህ ላይ ነበር ምስጢሩ የራሱን ጉድጓድ ቆፍሮ የራሱን ሕይወት
የሸሽገው:: ያን ሁሉ ስቃይና ችግር የማውቀው እኔ ብቻ ነኝ» ብዩ በልበ ሙሉነት እንደገና ተዝናናሁ፡፡
አባቴ ስቅላት እንደ ተፈረደበት ሰው ወዙ ደረቅ። እርሱ በተደፈርኩ
ባይነት፣ እናቴና እኅቴ በድንጋጤ እንደ ተጨነቁ እኔም የዓላማዬን መጨረሻ ለማሳመር ሳሰላስል በቤቱ ስጥ ጊዜያዊ ጸጥታ ሰፈነ። የአባቴን ሕሊና ለማንበርከክ፣ ሲጨቁነኝና ሲያፍነኝ የኖረውን የበላይነቱን ለመሰባበር እእምሮዬ
ሙሉ የማጥቃት ዝግጅቱን ቀጠለ።
«ልጨርስልሃ?» አልኩት የሐሳቤን ደጀን ካጠናከርኩ በኋላ፡፡
«ደግሞ ምን ቀረህ? ምን ቀረኝ ልትል ይሆን?»
«እኔ የማሳይህና የማሳውቅህ ወርቁን ብቻ ሳይሆን የወርቁንም ማዕድን ጭምር ነው::
“ይኻ ሁሉ ዝብዝብ ምን ለማለት ፈልገህ ነው?»
«ባጭሩ ላስረዳህ እችላለሁ፡ የዚህ ልጅ እናት የወዲያነሽ አሸናፊ ያን ሁሉ መከራና ሥቃይ ካሳለፈች በኋላ እንደገና ከእኔ ጋር ትገናኝተን በአሁኑ ጊዜ እጅግ የማከብራትና የምወዳት ባለቤቴ ነች!! »
«የወላዲተ አምላክ ያለህ! ምን? ምን አልክ አንተ!?» ብሎ እንደ ብራቅ ጮኸ፡፡ «የወዲያነሽ ሚስቴ ነች፡፡ የምንኖረውም አብረን ነው!» ብዩ በተመሳሳይ ጩኸት መለስኩለት፡፡
ከመቀመጫው ላይ በቁጣ ተነሥቶ «ውጣ! ውጣልኝ! ቅሌታም ክብረ ቢስ! ዘር አሰዳቢ! እንዴት አንተ! መድኃኒ ዓለም ያዋርድህ! ኧረ ሂድልኝ! አረ
ውጣልኝ! ክብረ ቢስ ዘር አሰዳቢ!» ካለ በኋላ ማንቁርቱን የታነቃ ያህል ድምፁ እየሰለለ «አንዳንድ ያልተባረካ ሽንት ይኸው ነው! ያህያ ሥጋ...» ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ፊቱ ፍም መስሎ ተጨማደደ፡፡ ጭንቅላቱ ላይ በመሸጎሪያ እንደ ተመታ ሰው መኻል አናቱን በቀኝ እጁ መዳፍ ጫን ብሉ አቀርቅሮ ተቀመጠ።
እውነት በዙሪያው ተጎማለለች! ከአጭር የዝምታ ቆይታ በኋላ ዐይኑ ቀይ ሽንኩርት መስሎ እንደ ሰካራም ተግተርትሮ ተነሣና «ሰበብ አትሁንብኝ! ካህያህም ከውርንጭላህም ጋር ገደል ግባ!! » ብሎ ወደፊት ራመድ አለ።
አልተነቃነቅሁም፡፡ አልተጠጋም፡፡ ነገር እንደሚያጣራ ሰው ከወደ ትከሻው ሰገግ ብሎ አንገቱን ሰብሮ ቆመ፡፡ በቁጣ የታግለበለበው ደሙ በግንባሩ ላይ አሽቆለቆለ። ፊቱ የጋለ የመቆስቆሻ ብረት መሰለ። እህቴና እናቴም ቁንጢጥ እንደ ተጠሩ
ሕፃናት ተርበተበቱ። ጋሻዬነህ በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ ጨምድዶ ያዘኝ።
ልጄን በተዝናና ወኔ አቅፌ «አዎ ብትወዱም ብትጠሉም የወዲያነሽ ባለቤቴ ናት! ሕዝብ አሕዛብ እንዲሰማና እንዲያውቅ አደርጋለሁ፡፡ የሀብታምና
የከበርቴ ልጅ ብትሆን ኖሮ ይህ ሁሉ የተቃለለውና የተዋረደው አጥንቷ ልዩ ስምና ክብር ይሰጠው ነበር። እንኳን እናንተ እኔ ራሴ የገፈፍኳትንና የነጠቅኋትን
መብትና ነጻነት ታገኛለች፡፡ ይህ የውዴታ ጉዳይ አይደለም። ጤዛ የምታህለዋን ጣጣ ስትፈሩ ተራራ የሚያህል መከራ ይጠብቃችኋል። አሁንም በድጋሚ የማረጋግጥልህ የወዲያነሽ የምወዳት ባለቤቴ ናት:: የአብራኬ ክፋይ! የጋሻዬነህ
እናት ናት!» ብዩ ተጎማለልኩ።
«በሕግ! በሕግ አምላክ ውጣልኝ! ዛሬ ጉድ ይፈላል! አስወጡልኝ
ብያለሁ!» ብሎ ተመልሶ ተቀመጠ የትንሽ ትግል ፍጻሜና የአነስተኛ ፍልሚያ መደምደሚያ ሆነ፡፡
ጋሻዬነህን ይዤ ወደ ውጭ ስወጣ የወዲያነሽ ከምድር ቤቱ በር አጠገብ ከለል ብላና ዐይኗን በድንጋጤ በሰፊው ከፍታ «ምናሉህ? የእኛ ነገር እንደምን
ሆነ? ፍሬ ነገሩ አይሰማም እንጂ ስትጫጨሁ ነበር» ብላ ፍርሃት በተጠናወተው መልስ ጠባቂ ስሜት ጠየቀችኝ፡፡ ሁሉም ነገር እንዳሰብኩትና እንደ ፈለግሁት
ሆነ። ፍርሃትንና የበታችነትን እንዲሁም የሕሊና ባርነትን ተቋቁሜያቸዋለሁ፡፡
እንዲያውም እየደመሰስኳቸው ነው። አትፍሪ! እኒ ምንጊዜም ቢሆን አብሬሽ አለሁ። የሚለያየን ምንም ኃይል አይኖርም፡፡ የእኒንና የአንቺን ዘላቂ አንድነት የሚጠሉና የሚቃወሙ ሁሉ ጠላቶቻችን ናቸው። እንዳንቺ በመከራ ማጥ ውስጥ የሚሠቃዩና የተበደሉ ሁሉ አብረውን ይቆማሉ፡፡ በአባቴ ቤት ብቻ ሳይሆን በመሰሎቹ ፊት ሁሉ እየቆምን ማንነታችንን እናስመሰክራለን። ይህ ከትልቁ
ዓላማና ረጂም ግብግብ ውስጥ ቅንጣቱ ቢሆንም ከእኛ ጋር ላለችውና ወደፊት ይበልጥ እየደመቀች ለምታይለው እውነት አንድ ርምጃ ነው:: ነይ እንሒድ!
ከእንግዲህ እኔና አንቺ የምናጠቃውም ሆነ የምንከላከለው በአንድነት ነው» ብዩ ቀኝ እጅዋን ይዤ ከምድር ቤት ወጣን።
እባክህ ይቅርብህ! በዘመድና በሽማግሌ ይሁን። በዚሁ ወደ ቤታችሁ ሒዱ» ብላ የውብነሽ በተሰበረ ሕሊና ለመነችኝ፡፡
ፊቴን በቁጣ ከሰከስኩና "የመጣንበትን ጉዳይ ከፍጻሜ ሳናደርስ አንሔድም። ከእንግዲህ ወደፊት እንጂ ወደ ኋላ አንመለስም። እንደ ዛፍ ቀጥ
እንጂ እንደ ምድር እንቧይ አፈር መሳስ የለም፡፡ ይዣት እገባለሁ። የዛሬዋን ዕለት ዕቅዴን ከፍጻሜ አድርሼ በሙሉ የሕሊና ነጻነትና ድል እንመለሳለን ዕቅዱን ነገርኳት አመዳይ እንደ መታው እህል ገረጣች።
የወዲያነሽ የንግግራችን ጠቅላላ ይዘት ስላልገባት የውብነሽ ምንድነው የምትልህ?» ብላ ትኩር ብላ አየችኝ:: አቅጣጫችሁን ለውጡ፡፡ መሬት ሳሙ፡ ጫማ ላሱ ነው የምትለን፡፡ እኔ ግን መሽቆጥቆጥ ይበቃናል፡ ለሥቃይሽና ለበታችነትሽ የማብቂያ ድንበር እንሠራለታለን፡፡ የራሣችንን መብት በትግል
ማሳወቅ እንጂ መለመንና ማጎብደድ የለብንም። የሚበድሉንና የሚጨቁኑንን
ሁሉ እውነትን ይዘን እንጋፈጣቸዋለን እላለሁ:: እኔ የአንቺን የየወዲያነሽን ያህል
ያልተበደልኩና ያልተጨቆንኩ ብሆንም በአዕላፋት የጠላት ሠራዊት መካከል አንዱን ብቻ መግደል ጠላትን ድል ”ማድረግ አይደለም። ቢሆንም » ብዬ ገና
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሶሰት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ስደበኝ! ወይ መቆየት! አሁንሜ ብለህ ብለህ ስለ ሕጉ አስተያየት ሰጪና እርማት አቅራቢ ሆንክ! ስንት ሊቃውንት የደከሙበትንና ያረቀቁትን ሕግ አንተ ስላቃለልከው አይቀልም።
መንገርስ ልክ ልክህን እነግርህ ነበር፡፡ ዳሩ ምን ያደርጋል ይልቅ ወሬሀን ጠርቅ!".ብሎ የሚሆነውን እያሳጣው በቅምጡ ተቁነጠነጠ፡፡ ሕሊናው ጉዳዩን ቢረዳም
በፈቃደኛነት እንደማይረታ፣ በጨቋኝነት የተሞላ ሕሊናው በቀላሉ እጁን እንደማይሰጥ አወቅሁ፡፡ ቢሆንም የእኔ ሕሊናና ወኔ እየሞቀና እየጎለመሰ ሲሔድ
ያ በከንቱ ግብዝነት የተወጠረው የእርሱ ሕሊና ግን ቁልቁል ሲሟሽሽ ታየኝ።
በዚሀ ልጅ እናት ላይ..» በማለት እንደገና ቀጠልኩ፡፡ «በከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የመኻል ዳኛ ሆነህ አምስት ዓመት እስራት ፊርደሀባት ነበር፡፡ በሕይወቷ ውስጥ አምስት ዓመት ብቻ ሳይሆን የሕይወቷ ብዙ
ክፍል እንዲበላሽና እንዲሰናከል ተደርጓል። ወደ ዋናው ፍሬ ነገር ልመለስና በሕግና በእውነት» ስም በተቋቋሙት ፍርድ ቤቶቻችሁ ወንጀለኛ እያላችሁ ከምትፈርዱባቸው ንጹሐን ሰዎች ይልቅ በእናንተ እጅግ ጉልህ በሆነ ጥፋትና በሚጨበጥ ኃጢኣት ወንጀለኛ በሆናችሁት ሰው በላ ሰዎች የተሞላ ነው:: ወደ ልጄ ጉዳይ ልመለስና፣ ይህ ልጅ በዕጓለ ማውታ፣ እናቱ ወህኒ ቤት ውስጥ እየማቀቀች ሳይተያዩና ሳይገናኙ በጠቅላላው አምስት ዓመት ተለያይተው ቆይተዋል፡፡ እዚህ ላይ ነበር ምስጢሩ የራሱን ጉድጓድ ቆፍሮ የራሱን ሕይወት
የሸሽገው:: ያን ሁሉ ስቃይና ችግር የማውቀው እኔ ብቻ ነኝ» ብዩ በልበ ሙሉነት እንደገና ተዝናናሁ፡፡
አባቴ ስቅላት እንደ ተፈረደበት ሰው ወዙ ደረቅ። እርሱ በተደፈርኩ
ባይነት፣ እናቴና እኅቴ በድንጋጤ እንደ ተጨነቁ እኔም የዓላማዬን መጨረሻ ለማሳመር ሳሰላስል በቤቱ ስጥ ጊዜያዊ ጸጥታ ሰፈነ። የአባቴን ሕሊና ለማንበርከክ፣ ሲጨቁነኝና ሲያፍነኝ የኖረውን የበላይነቱን ለመሰባበር እእምሮዬ
ሙሉ የማጥቃት ዝግጅቱን ቀጠለ።
«ልጨርስልሃ?» አልኩት የሐሳቤን ደጀን ካጠናከርኩ በኋላ፡፡
«ደግሞ ምን ቀረህ? ምን ቀረኝ ልትል ይሆን?»
«እኔ የማሳይህና የማሳውቅህ ወርቁን ብቻ ሳይሆን የወርቁንም ማዕድን ጭምር ነው::
“ይኻ ሁሉ ዝብዝብ ምን ለማለት ፈልገህ ነው?»
«ባጭሩ ላስረዳህ እችላለሁ፡ የዚህ ልጅ እናት የወዲያነሽ አሸናፊ ያን ሁሉ መከራና ሥቃይ ካሳለፈች በኋላ እንደገና ከእኔ ጋር ትገናኝተን በአሁኑ ጊዜ እጅግ የማከብራትና የምወዳት ባለቤቴ ነች!! »
«የወላዲተ አምላክ ያለህ! ምን? ምን አልክ አንተ!?» ብሎ እንደ ብራቅ ጮኸ፡፡ «የወዲያነሽ ሚስቴ ነች፡፡ የምንኖረውም አብረን ነው!» ብዩ በተመሳሳይ ጩኸት መለስኩለት፡፡
ከመቀመጫው ላይ በቁጣ ተነሥቶ «ውጣ! ውጣልኝ! ቅሌታም ክብረ ቢስ! ዘር አሰዳቢ! እንዴት አንተ! መድኃኒ ዓለም ያዋርድህ! ኧረ ሂድልኝ! አረ
ውጣልኝ! ክብረ ቢስ ዘር አሰዳቢ!» ካለ በኋላ ማንቁርቱን የታነቃ ያህል ድምፁ እየሰለለ «አንዳንድ ያልተባረካ ሽንት ይኸው ነው! ያህያ ሥጋ...» ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ፊቱ ፍም መስሎ ተጨማደደ፡፡ ጭንቅላቱ ላይ በመሸጎሪያ እንደ ተመታ ሰው መኻል አናቱን በቀኝ እጁ መዳፍ ጫን ብሉ አቀርቅሮ ተቀመጠ።
እውነት በዙሪያው ተጎማለለች! ከአጭር የዝምታ ቆይታ በኋላ ዐይኑ ቀይ ሽንኩርት መስሎ እንደ ሰካራም ተግተርትሮ ተነሣና «ሰበብ አትሁንብኝ! ካህያህም ከውርንጭላህም ጋር ገደል ግባ!! » ብሎ ወደፊት ራመድ አለ።
አልተነቃነቅሁም፡፡ አልተጠጋም፡፡ ነገር እንደሚያጣራ ሰው ከወደ ትከሻው ሰገግ ብሎ አንገቱን ሰብሮ ቆመ፡፡ በቁጣ የታግለበለበው ደሙ በግንባሩ ላይ አሽቆለቆለ። ፊቱ የጋለ የመቆስቆሻ ብረት መሰለ። እህቴና እናቴም ቁንጢጥ እንደ ተጠሩ
ሕፃናት ተርበተበቱ። ጋሻዬነህ በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ ጨምድዶ ያዘኝ።
ልጄን በተዝናና ወኔ አቅፌ «አዎ ብትወዱም ብትጠሉም የወዲያነሽ ባለቤቴ ናት! ሕዝብ አሕዛብ እንዲሰማና እንዲያውቅ አደርጋለሁ፡፡ የሀብታምና
የከበርቴ ልጅ ብትሆን ኖሮ ይህ ሁሉ የተቃለለውና የተዋረደው አጥንቷ ልዩ ስምና ክብር ይሰጠው ነበር። እንኳን እናንተ እኔ ራሴ የገፈፍኳትንና የነጠቅኋትን
መብትና ነጻነት ታገኛለች፡፡ ይህ የውዴታ ጉዳይ አይደለም። ጤዛ የምታህለዋን ጣጣ ስትፈሩ ተራራ የሚያህል መከራ ይጠብቃችኋል። አሁንም በድጋሚ የማረጋግጥልህ የወዲያነሽ የምወዳት ባለቤቴ ናት:: የአብራኬ ክፋይ! የጋሻዬነህ
እናት ናት!» ብዩ ተጎማለልኩ።
«በሕግ! በሕግ አምላክ ውጣልኝ! ዛሬ ጉድ ይፈላል! አስወጡልኝ
ብያለሁ!» ብሎ ተመልሶ ተቀመጠ የትንሽ ትግል ፍጻሜና የአነስተኛ ፍልሚያ መደምደሚያ ሆነ፡፡
ጋሻዬነህን ይዤ ወደ ውጭ ስወጣ የወዲያነሽ ከምድር ቤቱ በር አጠገብ ከለል ብላና ዐይኗን በድንጋጤ በሰፊው ከፍታ «ምናሉህ? የእኛ ነገር እንደምን
ሆነ? ፍሬ ነገሩ አይሰማም እንጂ ስትጫጨሁ ነበር» ብላ ፍርሃት በተጠናወተው መልስ ጠባቂ ስሜት ጠየቀችኝ፡፡ ሁሉም ነገር እንዳሰብኩትና እንደ ፈለግሁት
ሆነ። ፍርሃትንና የበታችነትን እንዲሁም የሕሊና ባርነትን ተቋቁሜያቸዋለሁ፡፡
እንዲያውም እየደመሰስኳቸው ነው። አትፍሪ! እኒ ምንጊዜም ቢሆን አብሬሽ አለሁ። የሚለያየን ምንም ኃይል አይኖርም፡፡ የእኒንና የአንቺን ዘላቂ አንድነት የሚጠሉና የሚቃወሙ ሁሉ ጠላቶቻችን ናቸው። እንዳንቺ በመከራ ማጥ ውስጥ የሚሠቃዩና የተበደሉ ሁሉ አብረውን ይቆማሉ፡፡ በአባቴ ቤት ብቻ ሳይሆን በመሰሎቹ ፊት ሁሉ እየቆምን ማንነታችንን እናስመሰክራለን። ይህ ከትልቁ
ዓላማና ረጂም ግብግብ ውስጥ ቅንጣቱ ቢሆንም ከእኛ ጋር ላለችውና ወደፊት ይበልጥ እየደመቀች ለምታይለው እውነት አንድ ርምጃ ነው:: ነይ እንሒድ!
ከእንግዲህ እኔና አንቺ የምናጠቃውም ሆነ የምንከላከለው በአንድነት ነው» ብዩ ቀኝ እጅዋን ይዤ ከምድር ቤት ወጣን።
እባክህ ይቅርብህ! በዘመድና በሽማግሌ ይሁን። በዚሁ ወደ ቤታችሁ ሒዱ» ብላ የውብነሽ በተሰበረ ሕሊና ለመነችኝ፡፡
ፊቴን በቁጣ ከሰከስኩና "የመጣንበትን ጉዳይ ከፍጻሜ ሳናደርስ አንሔድም። ከእንግዲህ ወደፊት እንጂ ወደ ኋላ አንመለስም። እንደ ዛፍ ቀጥ
እንጂ እንደ ምድር እንቧይ አፈር መሳስ የለም፡፡ ይዣት እገባለሁ። የዛሬዋን ዕለት ዕቅዴን ከፍጻሜ አድርሼ በሙሉ የሕሊና ነጻነትና ድል እንመለሳለን ዕቅዱን ነገርኳት አመዳይ እንደ መታው እህል ገረጣች።
የወዲያነሽ የንግግራችን ጠቅላላ ይዘት ስላልገባት የውብነሽ ምንድነው የምትልህ?» ብላ ትኩር ብላ አየችኝ:: አቅጣጫችሁን ለውጡ፡፡ መሬት ሳሙ፡ ጫማ ላሱ ነው የምትለን፡፡ እኔ ግን መሽቆጥቆጥ ይበቃናል፡ ለሥቃይሽና ለበታችነትሽ የማብቂያ ድንበር እንሠራለታለን፡፡ የራሣችንን መብት በትግል
ማሳወቅ እንጂ መለመንና ማጎብደድ የለብንም። የሚበድሉንና የሚጨቁኑንን
ሁሉ እውነትን ይዘን እንጋፈጣቸዋለን እላለሁ:: እኔ የአንቺን የየወዲያነሽን ያህል
ያልተበደልኩና ያልተጨቆንኩ ብሆንም በአዕላፋት የጠላት ሠራዊት መካከል አንዱን ብቻ መግደል ጠላትን ድል ”ማድረግ አይደለም። ቢሆንም » ብዬ ገና
❤1👍1