አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?


አሁንም ግፍ አይበቃሽም
ዘንድሮም ለምለም ትያለሽ
ካቀፍሽው ቅጠል ባለፈ
የለመለመ ምን አለሽ?

ካቻምናም አምናም መተሻል
አቅፈንሽ አጥነን ደግሰን
አመትሽ ውበቱ ላይቆይ
እያደር ሊያተራምሰን

አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?

አምና ተስፋ አስደረግሺኝ
ደክሜ ቤቴን ሰራሁኝ
አልቅሼ ልገባበት ስል
ይፈርሳል ሁሉ ሰማሁኝ
አሁንም ተስፋ አልቆረጥኩም
ቃልሽን ስመላልሰው
አመትህ ተባርኳል ብለሽ
የላክሺኝ እንደ ሞኝ ሰው
ስታገል ከማይሽር ህይወት
መቀመቅ ነፍሴን ሲውጣት
ወደፊት ፈቀቅ እያልኩኝ
ሞት ልቤን እንዳይለውጣት

"አበባ አየሆሽ" አትበዪኝ
አበባ አልቸገረኝም
ዘፈንሽ አንገሽግሾኛል
ጨዋታሽ አይሰማኝም
በያመት ደምቀሽ ስትመጪ
ህፃን ልጅ ለምትመስዪው
ግጥሙን በምነግርሽ ቃል
ስትዘፍኚ አስተካክዪው

"የሀገሬ ልጆች ውጡ በተራ
ቅስም ሰብሬ  ሰው እስክሰራ
እንኳን ሰውና  የለኝም እድል
ሁሌ መጣለው አመት ላጎድል
አመት አጉድዬ ስገባ ቤቴ
ደስታ ይሰማታል የእንጀራ እናቴ"
አደዪ
የሞት ጉዳዪ
"ኡኡ" በዪ

እንደዚህ ብለሽ ዝፈኚ
ግጥሙን አስተካክለሽው
በቃ አንቺም እንዳገሬ ሰው
ጊዜን ነው የተማመንሽው?

"ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ
ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ"

ሆሆሆሆ!

አታፍሪም ደግሞ
ልክ እንደ ንፁህ እንዳልበደለ
ተስፋሽ ምስኪኑን እየገደለ
ከዘመን ዘመን ማትለወጪ
ጉድ ያዘለ አመት አቅፈሽ ምትሰጪ
ሆ ብለሽ መጣሽ?
ሆ ብለሽ ውጪ!

ለተድላ ሳይሆን
ለሞት ዋዜማ ፡ እያስጨፈርሺኝ
በመጣሽ ቁጥር
ሆ የምልልሽ ፡ ሞኝ አደረግሺኝ?

አሁን ንገሪኝ
ስለ አመትሽ
ይብስብኛል ወይስ ድናለው?
ዘፈኑን ተዪ ፡ ያንቺን ስሞታ ለምጄዋለው

ባለእንጀሮችሽ በተራ ገቡ
አዝማች አባትሽ ሌላ አገቡ
እንጨቱን ሰብረሽ ቤት እስክትሰሪ
ለእንጀራ እናትሽ ሳትናገሪ
እድጅ አድረሻል ኮከብ ስትቆጥሪ

እኔ ምስኪኑ

ምን ያገባኛል ስላንቺ ኮከብ
ምን ያገባኛል የእንቅልፍሽ ማጠር
የኔ ችግር ነው ወሰን የሌለው
የኔ ስቃይ ነው  የማይቆጠር

እህት አበባ  ፡ እህት አበባ
እህት አበባ  ስትልሽ ከርማ፤
ጥላሽ ብትሄድም በሀምሌ ጭለማ
እኔ ላይ "አዬዬ".. አትበዪብኝ፡
ለኔ አመቱ ነው  የጨለመብኝ።

ተይ ባለጊዜ..
ተይ እንቁጣጣሽ..
ሀገር ጉድ አቅፈሽ ፥
ሁሌ እየመጣሽ፦

እንኩ አትበዪን፡

ሀዘን ቁስላችን ፡ ድኖ ሳይገግም፤
ካምናው የሚብስ
ሌላ አዲስ አመት ..አንፈልግም!

🔘ሚኪያስ ፈይሳ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢128👏3
#ሲያጋጥም

ልቤ በግኖ ነዶ ራሴን በፎከትኩት
ሌላኛ ጠላቴን ቅማሌን ገደልኩት፡፡


#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😁8👍3😢1
"ሰሎሜ አንተን ሁለቴ ከድታሀለች ..ከማንም አስበልጣ ብታፈቅርህም ልብህን ግን ደጋግማ ሰብራዋለች። ከእኔ መወለድ በፊትም ሆነ ከእኔ መወለድ በኋላ ያደረገችብህን ነገር ቂም በሆድህ ቆጥርህ ነበር፡፡ያንን ይቅር ማለት እና መርሳት አልቻልክም፣ ጁኒየር ግን እንደአንተ ስላልሆነ እሷን በደስታ ነው የተቀበላት ፡፡ ቀስ በቀስም ትኩረቷን ማግኘት ጀመረ እና ጥረቶቹ ውጤት አስገኙለት… አንተን ረስታ ከእሱ ጋር ፍቅር እንደያዛት ስታስተዋል ከነከነህ፣ይባስ ብለው ሊጋቡ እንደሆነ ደረስክበት ….ከዛ ምን አደረክ ቀጥታ ገድለሀት ከእነሱ አንዳቸው እንደገደሏት እንዲያስቡ አደረክ ወይስ ምን አይነት የበቀል ዘዴ ነው የተጠቀምከው…..?ምን አልባት እናቴን ብቻ ሳይሆን ጁኒዬርንም ተበቅለኸው ይሆናል…?››

"በጣም ጥሩ አቃቢ ህግ ነሽ።በእውነት አድናቂሽ ነኝ…. ግን በዚያ መላ ምትሽ ትልቅ አመክንዬ ጥሰት አለበት፡፡››አለና የተቀመጠበትን ኩርሲ ወደእሷ አስጠጋ ….ምን ሊያደርግ ነው በሚል ስጋት በትኩረት ተመለከተችው፡፡

"አንቺ ..በብዙ ግምቶች እየተወዛገብሽ ነው…አንዱንም ማረጋገጥ አትችይም…በእኔ ላይ ምንም መረጃ የለሽም…ስለዚህ, ለምን የሁላችንንም ህይወትን ቀላል አታደርጊልንም ››አለና እጆቹን ትከሻዋ ላይ ጭነ… ወደራሱ ጎተተና ጉንጮን ሳማት፡፡
"ምክንያቱም አልችልም።›› ከንግግሯ በስተጀርባ ያለውን የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰማ እና እሷን ለመስበር ከግማሽ በላይ መንገድ ላይ እንደደረሰ አወቀ።

"ለምን አትችይም?" ጠየቃት፡፡

‹‹ምክንያቱም እናቴን የገደላትን፤መገደሏን አውቆ ገዳዩን ለመታደግ የተባበረውን በጠቅላላ መቅጣት እፈልጋለሁ።››
እጁን ከትከሻዋ ላይ አነሳና …አይን አይኗል በትኩረት እያየ….."ይህን ለሰሎሜ ብለሽ አይደለም እያደረግሽ ያለሽው… ለራስሽ ነው የምታደርጊው"አላት፡፡

"ያ እውነት አይደለም!"

" አያትሽ በጭንቅላትሽ ውስጥ የፈጠረችብሽ የማይሆን ሀሳብ አለ ፡፡እናም በእናትሽ ህይወት ውስጥ በተሳሳተ ጊዜ በመምጣትሽ እና ኑሮዋን በማበላሸትሽ ራስህሽ ይቅር ማለት አልቻልሽም።"

"በፈጣሪ አንተው ነህ ስለ ስነ ልቦና ግጭት ለእኔ የምታወራው?" ብላ በቁጣ ጠየቀችው። ቀጠለችናም "ገመዶ ራስ ወዳድ መሆንህን ለማወቅ ስለአንተ በቂ እውቀት አለኝ። ሌላ ሰው እንደግል ንብረትህ ስለምትቆጥር  ሲነኩብህ ትበሳጫለህ ።››

"አገላለጿ  ፈታኝ ነበር። ››
"ገመዶ ፣እናቴን ይቅር ለማለት በጣም የከበደህ ነገር ለምንድን ነው? እሷ ከሌላ ወንድ ጋር ስለተኛች ነው? ወይስ እድሉ እያለህ እሷን ባለማግባትህ ራስህን ይቅር ማለት አልቻልክም?"
ገላዋን በእጁ ነቀነቀ፣ ከዚያም እስኪነካኩ ድረስ ወደ ፊት አዘነበለ። "አንድ ጊዜ አስጠንቅቄሻለሁ ….እናትሽ ከጁኒየር ጋር የነበራትን ግንኙነት ለማስቀጠል እና ለምን እንደዛ እሷን ሊያፈቅራት እንደቻለ ለማወቅ ያለሽን የማወቅ ጉጉት ማርካት እየጣርሽ ነው"

"አይ ..ያ እውነት አይደለም" ብላ በቁጣ ካደች

" አይመስለኝም።"

‹‹ አንተ ታመሃል…?"አለችው፡፡

አንገቱን ጎንበስ አድርጎ ሳማት። በዝምታ ተቀበለችው….ከንፈሮቹን ወደከንፈሯ አስጠጋት…
…ባለችበት ሳትነቃነቅ ጠበቀችው፡፡ ከንፈሮቾን በስሱ ይመጣቸው ጀመር … ከንፈሯቾ እርጥብ እና ሙቀት የሚረጩ ከመሆናቸውም በላይ ጣፋጭ ነበሩ፣ ቀኝ እጁን አንቀሳቀሰና
በለበሰችው ሹራብ ውስጥ ሰቅስቆ ጡቷን በእጁ ጨመቀ። የጡቷን ጫፎች በሁለት ጣቶቹ ማፍተልተል ጀመረ… ጩኸት የተቀላቀለበት የጣር ድምፅ ከጉሮሮዋ ወጣ።አንገቱን ቀና አደረገና ቁልቁል ፊቷን ተመለከተ። በእጁ መዳፍ ውስጥ ተፈጥርቃ እንደተያዘች ትንሽ የዱር ፍጡር ልቧን ሲንፈራገጥ ይሰማዋል። አይኖቿ ተጨፍነው ነበር። መልሶ ከንፈሯን ጎረሰ…ምላሱን ወደውስጥ ከተተ…ከተቀመጠችበት ኩርሲ ተንሸራተተችና ደረቱ ላይ ተለጠፈችበት….ከተቀመጠበት ተነስቶ ልክ እንደህጻን ልጅ አቅፎ ወደቤቱ ውስጥ ይዞት ሄዶ አልጋው ላይ ሊዘርራትና ያለምንም ገደብ ሙሉ በሙሉ ከእሷ ጋር ለመቅለጥ እና ከእሷ ጋር ለመጥፋት ከፍተኛ ፍላጎት ጉሮሮዋ ስር ተሰነቀረበት…..እንደዚህ ካደረገ ወደኃላ መመለስ እንደማይችል እና ምንም ነገር እስከአሁን እንደነበረው እንዳማይሆን ያውቃል፡፡ምን ያድርግ…ልቡና አእምሮው ከፍተኛ ፊልሚያ ላይ ገቡበት፡፡ በመጨረሻ አእምሮው በልቡ ተሸንፎ እሷን ወደውስጥ ተሸክሞ ሊገባ ሲንቀሳቀስ የውጭ በራፍ በሀይል ሲንኳኳ ሰማ….ሁለቱም ከገቡበት መደንዘዝ እኩል ነቁ…..የበራፉ መንኳኳት ቀጠለ….ገመዶና አለም ተላቀቁ….ከተቀመጡበት የተዘበራረቀ ልብሷንና የተጎሳቆለ ፀጉሯን ማስተካከል ጀመረች….እሷ ሙሉ በመሉ እራሷን እንዳስተካከለች እርግጠኛ ከሆነ በኃላ በንዴት ሄዶ በራፉን ከፈተው..አቶ ፍሰሀ ነበር፡


ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
58👍13🔥4👎1
‹‹እኔ እንጃ …ትኑር አትኑር አይታወቅም..ሰው ልኬ  ነበር… ሲያንኳኩ ከውስጥ የሚመልስ ሰው የለም አሉኝ…ግን ምንድነው? የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ?››

‹‹ገመዶ ይህቺ የሰሎሜ ልጅ በጣም አደገኛ ነች..ቀድማ ጥቃት ጀምራለች….ሳታጠፋን የምታቆም አይመስለኝም››

‹‹ምን ተፈጠረ››

‹‹ቴሌግራምህን ክፈት የተፈጠረውን ልኬልሀለው….ዛሬውኑ አፍነን ወደተዘጋጀላት ቦታ መውሰድ አለብን…ቤት ካለች እንዳትለቃት ..እስክመጣ አብረሀት ሁን››ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡

ገመዶ መኪናውን ዳር አሲይዞ አቆመና ቴሌግራሙን ከፈተ …ከጁኒዬር አንድ ቪዲዬ ተልኳለታል፡፡

‹‹የሻሸመኔ ከተማ ወክሎ ለምክር ቤት የሚወዳደረው እጩ ተወዳዳሪው ስለእናቴ ግድያ ያውቃል!!››ይላል ርዕሱ…በንዴት እየተንቀጠቀጠ ከፈተው፡፡ሙሉ የአለም ምስል በእስክሪኑ ሞላ….፡፡በእናቷ እና በጁኒዬር..በእናቷ እና በገመዶ መሀከል ያለውን የልጅነት ግንኑኙነት ትዘረዝርና…እሷ እስከተወለደችበት ጊዜ ያለውን ታሪክ ተናግራ…ቀጣዩን ከሶስት ቀን በኃላ በተመሳሳይ ሰዓት ይጠብቁ በሚል ይቋረጣል፡፡ቪዲዬ ከተለቀቀ ገና አንድ ሰዓት ቢሆነውም..8 ሺ እይታ አግኝቷል…ከአንድ ከሁለት ቀን በኃላ በመላው ሀገር እንደሚዳረስ እርግጠኛ ነው…..ስልኩን ወደኪሱ አስገባና መኪናዋን አንቀሳቀሰ…አለም ቤት ጋር ሲደርስ ሳጂኑ በታዘዘው መሰረት በረንዳው ላይ ቆሞ እየጠበቀው ነበር፡፡

‹‹እ ምንም ነገር የለም››

‹‹አይ ምንም ነገር የለም››መለሰለት፡፡ኩማንደሩ ወደ ጓሮ ዞረ…ሳጅኑ ተከተለው….የጓሮውን በር ገፋ ሲያደርገው ተከፈተለት..ተንደርድሮ ወደውስጥ ገባ፡፡ በየክፍሉ እየተዘዋወረ ፈለገ…የለችም…መኝታ ቤቷ ገባና ቁም ሳጥኗን ከፈተ ባዶ ነው…ልብሷ ..ሻንጣዋ…ላፕቶፖ የለም፡፡አንድ ብጣሽ ወረቀት ጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል፡፡አነሳና ተመለከተው፡፡በንዴት ወደሳጅኑ ዞረና፡፡‹‹ምንድነው ኦና ቤት ነበር እንዴ ስትጠብቁ የነበረው?››

‹‹ ሄዳለች ማለት ነው››ሳጅኑ በድንጋጤ እና ግራ በመጋባት መልሶ ጠየቀ፡፡

‹‹ብሽቅ ናችሁ….››አለና በንዴት የፊት ለፊቱን በር ከፍቶ ወደበረንዳ ሲወጣ ጁኒዬር እየተንደረደረ ሲመጣ ተገጣጠሙ፡፡

‹‹አገኘሀት…?የት አለች?››

‹‹የለችም?››

‹‹የለችም ማለት?››

ኩማንደሩ ለጁኒዬር ሌላ መልስ ከመመለሱ በፊት ወደ ሳጅኑ ዞረና ‹‹ሳጅን በቃ አሁን አታስፈልግም..እዚህ ያላችሁ ስራ ተጠናቋል መሄድ ትችላለህ›› በማለት አሰናበተው፡፡

‹‹ግን እኮ መኪናዋ እንደቆመች ነው፡፡››
ገመዶ ‹‹መኪናዋን ከተጠቀመችማ በቀላሉ እንደምንከታተላት ታውቃለች..ለዛ ነው ማንም ሳያያት በጓሮ በር ወጥታ የተሰወረችው፡፡እቅዳችንን በሆነ መንገድ ያወቀችብን ይመስለኛል››ሲል ጥርጣሬውን ተናገረ፡፡

‹‹እንዴት ልታውቅ ትችላለች…?.ማን ሊነግራት ይችላል?››

‹‹አላውቅም…ግን እቃዎቾን ጠቅልላ ማንም ሳያይ በጓሮ በራፍ ወጥታ ነው የተሰወረችው….እና መኝታ ቤቷ ይሄንን ወረቀት ጥላ ነው ሄደችው..››አለና አንድ ብጣሽ ወረቀት አቀበለው፡፡

ለገመዶ..ጁኒዬርና ለአቶፍሰሀ….
እኔን ከዚህ ጫወታ ገለል ማድረግ እንደዚህ ቀላል አይሆንላችሁም፡፡ከዛሬ ጀምሮ ከፍትህ ይልቅ በቀልን መርጫለው፡፡ አድናችሁ ካገኛችሁኝ ግደሉኝ….ግን ያንን ማድረግ ከመቻላችሁ በፊት በየቀኑ አንድ አንድ ክንፋችሁን....ቀጥሎ እጆቻችሁን …ከዛም እግራችሁን… ከዛም አይኖቻችሁን..እያልኩ አጠፋችኋላው…..፡፡በማንኛውም ሰዓት ከመሀከላችሁ(ማለት..ገመዶ፤ጁኒዬር፤ስርጉት፤አቶ ፍሰሀ፤ሳራ)ከአምስታችሁ እናቴን የገደለው  ሰው  ወንጀሉን  አምኖ  አጅን  ለመንግስት  ከሰጠ በቀሌን  አቆማለው
….ካለበለዚያ ሁላችሁንም አጠፋችኋላው….የማስጀመሪያው ርችት ተተኩሷል …ሰዓቱ እየቆጠረ ነው…ለእኔም ለእናንተም መልካም እድል፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍42😱2218🔥1
ፈጣሪን ለማን ያሙታል

ቤተ መንግሥቱ ጀርባ ያለው ቅዱስ ገብርዔል ቤተክርስትያን አንዳንዴ አመሻሻ ላይ አርምሞውን፣ ድባቡን፣ የዛፎቹን ሽውታ ስለምወደው ጎራ እላለሁ።

ይሄ ምዕመን ጸሎቱ አድርገልህልኛል እና ተመስገን ነው፤ ይኼኛው አሳካልኝ ተማጽኖ ነው እያልኩ የምዕመናኑን ጸሎት ከሁኔታቸው አንጻር እገምታለሁ፡፡

እዚ የቤተክርስትያን ቅፅር : ግቢ ስገባ ነፍሴ እርጋታ ይሰፍንባታል።

ዛሬ...

ሁልጊዜ ስመጣ የምቀመጥበት ደረጃው ላይ ቁጭ ባልኩበት እማማ ጀማነሽ መጡ። ልጃቸው ከሞተባቸው አራት ቀን ሆኗቸዋል፡፡

እማማ ጀማነሽ ብቻቸውን ሲያወሩ፣ ሳንቲም ሲለምኑ፣ ትክዝ ኩርምት ብለው መሬት ሲጭሩ፣ ማንን እንደሆነ እንጃ ሲሳደቡ ብዙ ቀን አይቻቸዋለሁ፡፡ ሳንቲም ሙዳዬ ምጽዋት ውስጥ ሲከቱም ተመልክቼ አውቃለሁ።

ይለምናሉ። ካሏቸው ሦስት ልጆች ሁለቱ ልጆቻቸው ትንሽ አእምሯቸውን እንደሚያምባቸው አውቃለሁ፡፡

የልጃቸው ቀብር ቀን አይናቸው ላይ ትኩስ እንባ እንዳልታየ በትዝብት የልጃቸውን ስርዓተ ቀብር ቆመው ካለ ዋይታ፣ ካለ እንባ አንጀት የሚበላ ፊት እየታየባቸው እንዳስፈጸሙ ሰምቻለው።

እማማ ጀማነሽ ትንሽ ብቻ ራቅ ብለው አጠገቤ መጥተው ቁጭ አሉ። ሰውነታቸው ደልደል ያለ፣ ፊታቸው ጥብስብስ ያለ፣ ጸጉራቸው በሙሉ የሸበተ፣ ጉስቁልና እያንዳንዱ ዳናቸው ላይ ያረፈባቸው፣ አሮጌ ያደፈ ሙሉ ቀሚስ የለበሱ፣
ሰማያዊ እንደነበረ የሚያስታውቅ የመነቸከ ሻርፕ አድርገው፣ ባዶ እግራቸውን ሆነው መከራ ራሱን መስለዋል።

እማማ ጀማነሽ ትንሽ ቁጭ እንዳሉ አንጋጠው ወደ ሰማይእያዩ፦

“ልጄን ወሰድክ አይደል?! ክፋት ካልሆነ በቀር የሚያምብኝን እዮብን ወይ ሚኪን አትወስድም?!” አሉ።

"ክፉ ሆነህ እንጂ!! አቅም የሌለው ፍጡር ላይ እንዲህ ይጨከናል?! የፈጣሪስ ባሕሪ ነው? ስንት ሰው ለመዳን እየለመነህ እኔ ግደለኝ ስል እምቢ ትል ነበር?

ምግብ የቆለፈውን፣ ሲጮህ የሚውለውን ልጄን ትተህ ሁለት ቀን ያልታመመውን ልጄን ትቀማኛለህ? ለፍቶ፣ ሮጦ በፌስታል እህል የሚያመጣልንን ልጄን፣ አንድ ምርኩዛችንን መቀማት ምን ይባላል?!

እ?!

ፍጡርን ማምለጫ ማሳጣት ምን የሚሉት ጥበብ ነው? እንኳን በሕልውናህ የሚያምን ቀርቶ የካደህስ ቢሆን እንዲህ ይደረጋል?

ይደረጋል ወይ? ክፉ ሆነህ አንጂ!!! እንኳንስ ፈጣሪ በዚህ መጠን ፍጡርስ የወደቀን ለመጣል ይታገላል?!

ለማርያምስ ስንቴ ነገርኳት፤ ሕመሜን፣ እጦቴን እሷ ናት የሚገባት ብዬ ተሳልኩ፣ ለመንኩ፣ ምንም የለም?

በድዬም እንደ ሆነ ይቅር እንድትለኝ ለመንኩህ! ተማጸንኩህ!

መልስ የለም።

ደግሞስ ልበድል! ላጥፋ እኔ ብቻ ነኝ ኃጥያተኛ? ሌላው በሕግህ ስለሄደ ነው ብቻዬን የምሰቀለው?

አንተ ግን ማሰቃየት፣ ምርኩዜን መስበር አይደክምህም ?!"

ከዚህ በላይ የሚናገሩትን ቁጭ ብሎ ለመስማት ፈጣሪን ራሱን መሆን ሳያስፈልግ አይቀርም።

ጌታዬ፣ አንተ ግን እኔ እንደሰማኋቸው ስትሰማቸው ምን ብለህ ይሆን??


🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢278
‹‹ለእሷ ደህንነት ለመጨነቅ ምን የተለየ ምክንያት ያስፈልጋል…..አንዴ ስህተት ሰርተን እናቷን በጨቅላ እድሜዋ አሳጥተናታል….አሁን ደግሞ መልሰን እሷን ብንጎዳት ይቅር የሚባል ድርጊት አይሆንም..››

‹‹እና ምን ትላለህ…?.የሰራሁት ስህተት የምከፍልበት ጊዜ ደርሷል ..ከዚህ በላይ ቤተሰቤንም ሆነ በዙሪያዬ ያሉ ሰዎች ሲረበሹና ሲጎዱ ቁጭ ብዬ ማየት አልችልም፡፡››

‹‹ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው…?ምን ለማድረግ አስበህ ነው?፡፡››

‹‹በመጀመሪያ ነገ ጥዋት የፓርቲው ፅ/ቤት ሄጂ ከእጩነት እንዲያነሱኝና በእኔ ምትክ ሌላ ሰው እንዲተኩ ማመልከቻዬን አስገባለው፡፡ከዛ ቀጣዩን ደግሞ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አስብበታለው..ሶስተኛው ቪዲዬ ከመልቀቋ በፊት አንድ ሰው ኃላፊነቱን መውሰድና እሷንም ማቆም መቻል አለብን፡፡››

‹‹ልጄ ..እንዳልከው ከእጩነት እራስህን የማግለሉን ውሳኔ እኔም እቀበለዋለው…ከዛ ውጭ ግን በራስህ ምንም ነገር አታደርግም..እዚህ ጉዳይ ላይ ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ ሁላችንም አብረን ነበርን..አሁንም አብረን ነን … መደረግ ያለበትን ሁሉ ተነጋግረንና ተስማምተን ነው የምንወስነው፡፡››

‹‹አባዬ ለዛ የሚሆን ጊዜ እኮ የለንም››

‹‹አውቃለው…አታስብ ዛሬና ነገን የሆነ ነገር እናደርጋለን..በል አሁን ወደ ቤት ልሄድ ነው፡፡››

‹‹እሺ አባዬ እኔም የተወሰነ መስራት ያለብኝ ስራ አለ…ማታ እቤት መጣለው….››

‹‹ጥሩ ››አለና….ቢሮውን ለቆ በመውጣት ካለወትሮው መኪናውን እራሱ እያሽከረከረ ወደቤቱ ጉዞ ጀመረ፡፡

አቶ ፍሰሀ ቤቱ ከመድረሱ በፊት በጣም ተጨናነቀ … ወደአንድ ግሮሰሪ ጎራ አለና የሚፈልገውን መጠጥ አዞ እየተጎነጨ ይሄንን ከአልም ጋር ያለውን ችግር በምን ዘዴ ሊፈታው እንደሚችል ማሰላሰል ጀመረ..
….////

አለም እዛው ሻሸመኔ ከተማ በተከራየችው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ ሆና ጥግ ግድግዳ ታካ በተነጠፈች አንድ ሜትር ፍራሽ ላይ ጋደም ብላ በቀጣይ ማድረግ ስላለባት ነገር እያሰላሰለች ነው፡፡አሁን የመጀመሪያ በቀሏን ባሰበችው መንገድ አሳካታለች…ጁኒዬር ከተማዋን ወክሎ ለፌዴራል ህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት ለመግባት የነበረውን ሀሳብ ሰርዞ ከእጩነት እራሱን እንዲያገል ማድረግ ችላለች፡፡

በቀጣይ ደግሞ የበቀሏ ጅራፍ የሚለመጥጠው ኩማንደሩን ነው..እሱም ቢያንስ ስልጣኑን እንዲለቅና ከስራውም እንዲታገድ ማድረግ ነው የምትፈልገው…ከዚያም እንዲረዳት በቀጣይ እያዘጋጀች ያለችው በዩቲዬብ የሚለቀቀውን ሶስተኛ ቪዲዬ በእሱ ወንጀሎች ዙሪያ እንዲያጠነጥን እያደረገች ነው፡ሶሌ ኢንተርፕራይዝ ውስጥ ያለው ሚስጥራዊ የአክሲዬን ድርሻ ፤ እና ይሄንን ኢንተርፕራይዝ ለማሳደግ እድገትና ደህንት ለመጠበቅ ስልጣኑንና የመንግስትን ንብረት እንዴት አላግባብ ሲጠቀም እንደኖረ መረጃዎችን እያጠናከረችና እያደራጀች ነው፡፡

በቀጣይ ደግሞ ዳኛው ላይ ትዘምታለች..እሱም ለክብር ጡረታ ሳይበቃ ቀጥታ ከወንበሩ በውርደት ተሸቀንጥሮ ወደወህኒ እንዲወረወር ነው የምትፈልገው፡፡በመጨረሻ የአቶ ፍሰሀ ተራ ይሆናል፡፡ሁሉንም ቀስ በቀስ ክንፋቸውን በየተራ እየነቃቀለች በማድቀቅ መብረር የማይችሉ ተራ ሰው ታደርጋቸዋለች..አዎ እቅዷ እንደዛ ነው፡፡ሴቶቹን ለማጥፋት ጉልበቷን አታባክንም….ወንዶቹ ሲከስሙ እነሱም መደብዘዛቸው እና መንኮታኮታቸው አይቀርም…ከዛ በኃላ ምን አልባት ከተማውንም ሆነ ሀገሪቱን ለቃ ትሰደድ ይሆናል!!እዚህ ሀገር እንድትኖር የሚያበረታታ ምን ተዝታና ምን አይነት ተስፋ ይቀራታል?

ድንገት ብልጭ አለባትና ከተኛችበት ተነስታ ቻርጀር ላይ የነበረውን ስልኳን አነሳችና ክፍል ውስጥ ከነበረችው አንድና ብቸኛ አነስተኛ ጠረጴዛ ላይ ካሉ ከስምንት ከሚበልጡ ሲም ካርዶች መካከል አንዱን አነሳችና ስልኳ ውስጥ ከጨመረች በኃላ መደወል የምትፍገውን ቁጥር ፈለገችና ደወለች….ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡

‹‹ሄሎ…ማን ልበል?››
‹‹እኔ ነኝ ..ጋሽ ፍሰሀ››

‹‹ይቅርታ የእኔ እመቤት …አላወቅኩሽም››

‹‹እንደው ብትረሳ ብትረሳ ይሄን ድምፅ ትረሳለህ..እርግጠኛ ነኝ ከመደወሌ በፊት እራሱ ስለእኔ ነበር እያሰብክ ያለሀው››

‹‹አለም ነሽ እንዴ?››
‹‹በትክክል ተመልሷል››
‹‹እንዴት ነሽ…?የት ነሽ?››

‹‹ተው እንጂ ጋሽ ፍሰሀ… አሁን እዚህ ቦታ ነኝ ብዬ የምገኝበትን ቦታ የምነግርህ ይመስልሀል?ባይሆን አንተ የት ነህ…?መኪና እየነዳህ ይመስላል?፡፡››

‹‹አዎ …ምንም እልተሳሳትሽም..ስለአንቺ እያሰብኩ እየነዳው ቤቴን አልፌ ከተማውንም ለቅቄ ወደ  ባሌ ጎባ የሚወስደውን  መንገድ ይዤ እየነዳው ነው፡፡››
‹‹በዚህ ማታ… ሁለት ሰዓት እኮ ሆኗል….››

‹‹አላስተዋልኩም ነበር..አሁን እማ እዚህ ሶሌ መድረሴ ካልቀረ ወደ ደን ማሳዬ እየገባው ነው….እዚሁ አድሬ ጥዋት እመለሳለው..ደኑ ውስጥ ማረፊያ ጎጆ አለን››
‹‹አይ ጥሩ ነው…እንደውም እኔን እንዴት በቀላሉ አጥምደህ በእጅህ ማስገባት እንደምትችል የሆነ ሀሳብ ብልጭ ሊልልህ ይችላል…እንደዛ አይነት በደን የተሸፈነ ፀጥ ያለ ቦታ ለማሰብ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቼለው››

‹‹ጥሩ እየተዝናናሽብን ነው አይደል?››
‹‹አረ ምን በወጣኝ››

‹‹እሺ..አሁን ለምን ፈልግሺኝ››

‹‹እንዲሁ ናፍቀኸኝ….››

‹‹ምን  አልሽ…?ቆይ  ወይኔ  አውሬ  ገባብኝ…አውሬ….››የመርበትበት  ድምጹን  ተከትሎ ከፍተኛ የመንጓጓትና የፍንዳታ ድምፅ ተሳማ…በድንጋጤ ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤት

ውስጥ እየተዟዟረች ስልኩን ብትሞክር ይጠራል አይነሳም…..ምታደርገው ግራኝ ገባት
..ቀጥታ ቦርሳዋን ይዛ ከቤት ወጣች…ታክሲ ያዘችና መሄድ ወደማታስብበት ወደቀድሞ ቤቷ አመራች …እንደደረሰች ታክሲውን አሰናበተች እና ቀጥታ ወደግቢው ውስጥ ነው የገባችው…ምን አልባት የሆነ ከለላ ስር ተደብቆ የእሷን መምጣጥ የሚጠብቅ ሰላይ ሊኖር እንደሚችል ትገምታለች..ቢሆንም ግድ አልሰጣትም፡፡ቀጥታ ግቢ ውስጥ ወደቆመችው መኪናዋ ነው ያመራችው …ውስጥ ገባችና ሞተሩን አስነስታ እየነዳች ከግቢው ይዛ ወጣች
..ቀጥታ አቶ ፍሰሀ ወደነገራት አቅጣጫ መንዳት ጀመረች፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
56👍11🤩1
የላቸውም፡፡ከ10 ደቂቃ ትግል በኃላ በራፉ ተከፈተለት….እንደምንም እራሱን ጎትቶ ወጣና መሬት ላይ ተዘረረ….ከግንባሩ የሚንጠባጠብ ደም ተመለከተ…እጆቹ ሁለት ቦታዎች በመስታወት ስብርባሪ ተቆርጠዋል…እንደምንም ራሱን አጠናክሮ ተነስቶ ቆመ …በሰማዩ ላይ ጨረቃዋ በግማሽ ወጥታ የተወሰነ ብርሀን እየረጨች ስለሆነ ሙሉ በሙሉ ድቅድቅ ጨለማ አይደለም…ከቦታው ተንቀሳቀሰ እና ወደጫካው ውስጥ ገብቶ በግምት 20 ደቂቃ ያህል ወደሚያስኬደው አቋራጭ ጠባብ የእግር መንገድ ገባና ወደ ጎጆው መራመድ ጀመረ…፡፡

በሰላሙ ጊዜ እድሜውን ሙሉ ሲወጣ ሲወርድበት የኖረበት ጥቅጥቅ ጫካ ቢሆንም በዚህ ጊዜ ሁሉም ነገር የተለመደ እና አሰልቺ የሆነበት ይመስላል፡፡ በጫካው ውስጥ የሚገኙትን ግዙፍ የጥድ ዛፎች መቶ ዓመት ያስቆጠሩ ሊሆኑ ይችላል፣ እና እነዚህ በተለያዩ ቁጥቆጦዎች የተሸፈኑ ጥንታዊ ዛፎች ግንዶቻቸው በውስጣቸው የበሰበሱ ነበሩ። አንዳንድ ዛፎች ወድቀው ግዙፍና አስቀያሚ ሥሮቻቸውን ወደ ላይ ተፈንቅለው ይታዩ ነበር፣ እና የስሮቹ ቅርፃች በዛ ጭለማ ድንገት ላያቸው አስፈሪ ጭራቆች ስለሚመስሉ ቅፅበታዊ ፍራቻ በሰው ደም ውስጥ ይረጫሉ፡፡ አብዛኛው ደን ግን በለምለም የባህር ዛው ዛፎች ተጠቅጥቆ የተሞላ ነው፡፡

አቶ ፍሰሀ በጫካው ውስጥ የሚንሾሹትን ዛፎቹ እያቋረጠ እና የረገፉ ቅጠሎች በእግሮቹ እያንኮሻኮሸ ሰሞኑን aስላጋጠሙት ችግሮች እያሰላሰለ ጉዞውን ቀጥሏል። እንደዛም ቢሆን በውስጡ የነገሰው መጨነቅ፤ውዝግቦች፣ ብስጭቶች እና ጭንቀቶች በጫካው ታላቅነትና ጥንታዊ ኃይል የተዳከሙ ይመስሉ ነበር። ከወራት በፊት እሱ ልክ እንደብረት ጠንካራ እና ጤናማ ሰው ነበር፡፡ያቺ ሴት ወደእዚህ ከተማ መጥታ ፊት ለፊቱ ከተጋገረጠችበት ቀን አንስቶ ግን እንደቀድሞ ብርቱ ሆኖ መቀጠል አልቻለም…በሙሉ አቅም ሊፋለሟት የማይችሉት ጠላት ነው የሆነችበት፡፡ ሰሞኑን ስለእሱና ስለቤተሰቦቹ በዩቲዩብ የለቀቀችው ሁለት ተከታታይ ቪዲዬ ቅስሙን ሰብረውታል…ከቀናት በኃላ በቀጣዩ ቨዲዬ በሚለቀቁ መረጃዎች ሙሉ በሙሉ ከቁጥጥር ውጭ ከመውጣታቸው በፊት ማስቆም ባለመቻሉ ነበር ተስፋ የቆረጠው።

‹‹ይሄ ምልክት ነው ››ሲል አሰበ…
‹‹ከደቂቃዎች በፊት ሞት ፊት ለፊቴ ቆሜ ነበር…ከእነ ሚስጥሬ እና ከነ ሀጥያቴ ሞቼ ነበር…አምላክ አሳይቶ የማረኝ ነገሮችን በትክክለኛው መንገድ እንዳስተካክል ነው››ሲል አሰበ….ነገሮችን በትክክለኛው መንገድ ለማስተካከል ግን የግድ በውስጡ ለአመታት የቀበረውን ሚስጥር ለመላ ቤተሰቡ በግልፅ መናገር አለበት….ያንን ማድረግ ደግሞ ምን አልባት ብዙ ነገር ሊያሳጣው ይችላል፡፡በዚህ የመጨረሻ የእድሜ ዘመኑ የሚያፈቅራት ሚስቱ ሳራ ልትፈታው ትችለች…ልጁ ጁኒዬርም መቼም ይቅር ላይለው ይችላል….‹‹ቢሆንም ይሄ ሁሉ ቅጣት ይገባኛል››ሲል ነገሩን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ወሰነ፡፡እንደዚህ በመወሰኑ የሰውነት ቅጥቅጥ ጥዝጣዜ ነፍሱን ጭምር እያነሰፈሰፈው ቢሆንም ከብዙ ወራቶች ቁዘማ በኃላ እየተረጋጋ ሲሄድ ተሰማው ..ከዚህ ውሳኔ በኃላ ነው ድንገት ከጅቡ ጋር በትንሽ ርቀት ተፋጦ ራሱን ያገኘው፡፡ አውሬው ጋር ፊት ለፊት እየተያዩ ቆሙ። በአቶ ፍሰሀ ሰውነት የፍርሀት ቅዝቃዜ ፈሰሰ። ‹‹እንዴ አምላኬ የሰጠኸኝን የንሰሀ ጊዜ መልሰህ ልትነጥቀኝ ነው እንዴ?…አረ አታድርገው››ከአመታት በኃላ እውነተኛ ፀሎት ፀለየ፡፡

‹‹ ምን ማድረግ አለብኝ?››እራሱን ጠየቀ፡፡ድንገት ጎኑን ሲዳብስ ሽጉጡ መኖሩን ተመለከተ፡፡ቶሎ ብሎ አወጣውና በእጁ አስተካክሎ ያዘው፡፡ተኩሶ ለመግደል አልፈለገም፡፡ እሱ ራሱ ከደቂቃ በፊት ነፍሱ ከሞት በተአምር ተርፏል.. ምንም እንኳን እንስሳ ቢሆንም አሁን መልሶ ሌላ ነፍስ አያጠፋም…ወሰነ‹‹እግዜር ያተረፈኝ ነፍስ እንዳጠፋ አይደለም››

‹‹ዞር ብዬ መሮጥ አለብኝ?››ሲል ራሱን ጠየቀ.. በዚህ ዕድሜው በዛ ላይ እንዲህ ሰውነቷ ደቆ በጫካ ውስጥ ህይወቱን ለማዳን ሲሮጥ በአይነ ህሊናው ሳለው፡፡
‹‹ፍሰሀ በጭራሽ አትሮጥም፡፡›› ለራሱ ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ቀስ ብሎ ወደኃላው ማፈግፈግ ጀመረ…‹‹እውነት ነው፣ ጠላት ካንተ ሲበረታ አቅምን አውቆ ማፈግፈግ ብልህነት ነው። እና አንዳንዴ በጦርነት ጊዜ ሞኞች መንገድን ሲጠረቅሙት በብልጠት ከመንገድ ዞር ማለት ያስፈልጋል።››አለ፡፡

በራሳቸው የሚንከራተቱ ጅቦች በመንገዳቸው ላይ ያጋጠማቸውን ማንኛውንም ፍጥረት ሊያጠቁ እንደሚችሉ ከልምድ ያውቃል፡፡ በተለይ እንደተበደሉ ከተሰማቸው ቂመኞች እና ቁጡዎች ናቸው..አሁን ፊት ለፊቱ የተጋረጠው በጣም ወጣት ጅብ አይመስልም። እንስሳው ፍሰሀን በትኩረት ተመለከተው፣ ፍጹም የማይንቀሳቀስ ሆኖ ቆመ፣ አንድም ጊዜ እንቅስቃሴ አላደረገም።የሚንቀሳቀሰው ጅራቱ ብቻ ነው ። ለጥቃት ወይም ለማፈግፈግ በተከፋፈለ ልብ ተጨንቆ የነበረ ይመስላል?የሰው ልጅ ለመረዳት ቀላል ነበር፣ እና ሳያውቁ ጥቃት ካልደረሰበት እና ድንገት ከኋላው ቢላዋ ካልተሰካበት በስተቀር ራስን ለመከላከል ቀላል ነበር። ድንገተኛ ጥቃት ከሁሉ የከፋው ነበር ፡፡

‹‹እስከመቼ እንደዚህ ተፋጠን እንቆያለን?››መላሽ ባይኖርም ጠየቀ፡፡

እንስሳው ማጥቃት ሊጀምር መሰለ.. እና ዓይኖቹ ተጨፍነዋል…እና ሰውነቱ ሁሉ ሲወጣጠር በፊት ከነበረው የበለጠ ግዙፍ ሆኖ ታየ .፣ ዓላማው ገዳይ ለመሆን እቅድ ያለው አይመስልም ።ምናልባት ታሞ ይሆናል? እነዚህን የሩቅ ቁጥቋጦች ላይ በብቸኝነት ለመዝመት ፈልጎ ይሆን?

አቶ ፍሰሀ‹‹ በእውነት ወደ እዚህ ስፍራ የመጣኸው ለመሞት ከሆነ ንገረኝ ?››ሲል በውስጡ እንስሳው ላይ አጉረመረመ ፡፡

‹‹ተረድቼሀለው እና እውነቱን ማወቅ ከፈለግክ እኔ በአንተ በጣም በጣም እንደምቀና ልንግርህ ፈልጋለው። እኔም መሞት እፈልጋለሁ። አዎ እዚህ ጫካ ውስጥ. በፀጥታ ብሞት በጣም ደስተኛ ነኝ …ግን የሰራሁትን ከባድ ስህተት ማስተካከል አለብኝ፣ለዛ ደግሞ ጥቂትም ቢሆን ተጨማሪ ጊዜ እፈልጋለው። ››

በቅጽበታዊ ውሳኔ ሽጉጡን ወደሰማይ ከፍ አደረገና ቃታውን ተጫነና ሁለት ጥይቶች አከታትሎ ተኮሰ…. እንስሳው በሸኮናው መሬቱን በንዴት ቧጠጠ እና ራሱን ወደጫካው ወረወረ፣ ።አቶ ፍሰሀ በራሱ ብልህነት መገረሙን ማቆም አልቻለም። በአቅራቢያው ካለው ዛፍ ጀርባ ተወረወረ…ከዚያም ሸጉጡን እንደያዘ በጥድ በተሟላ ጥሻ ውስጥ ዘልቆ ገባና ተሸሸገ።በመጨረሻ ቆም ብሎ ሲያዳምጥ መንጋው ሆነው ወደእሱ እየመጡ መሰለው፡፡ የሰማው ነገር የመንጋ የእግር ኮቴ ሳይሆን የገዛ የልቡ ምቱ መሆኑን ለመረዳት ብዙ ጊዜ ወስዶበት ነበር። ደሙ ወደ ጭንቅላቱ ሽቅብ እየሮጠ ከመሆኑም በላይ በጆሮው አስፈሪ ጩኸት ይሰማው ጀመር….በአካባቢው ምንም አይነት የድሩ እንስሳት ድምጽ የለም። አውሬው አሁንም በመቶ ሜትር ርቀት ላይ ተሸሽጎ እየተነፈሰ ነው።አቶ ፍሰሀ መንገዱን አሳብሮ ተንቀሳቀሰ..አውሬው ሊከተለው አልደፈረም….ወዲያው የባትሪ መብራት በላዩ ላይ ሲወነጨፍ ተመለከተ….‹‹ማነው…?እባካችሁ እርዱኝ›› ድምጽ አውጥቶ ተማፀነ፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronosen
👍5027🤔4
#ባለመኖር_ስጋት

አብሬሽ እስካለሁ ''ፈልገሽ አትጪኝ''
ከሚል ምኞት በቀር ሌላ ሐቅ አላውቅም፣ በተፈለጉበት አለመኖር እንጂ
የሚፈልጉትን ማጣት ብዙ አይጨንቅም፡፡

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍62
አንድ የመስታወት ቁራጭ ከእንብርቷ በታች ሆዷ ላይ ተሸጦባት ነበር….ትንፋሿን ሳዳምጥ ትንሽ ትንሽ ብን ብን ይላል፡፡በደመነፍስ ስልኬን አውጥቼ ለአባዬ ደወልኩለት… ከዛ በኃላ የሆነውን እኔ አላውቅም….እራሴን ስቼ ቤት ክፍሌ ውስጥ ተዘግቶብኝ በሶስተኛው ቀን ነው የነቃሁት፡፡እና አውቄም ሆነ በድንገት አደጋ እናትሽን የገደልኳት እኔ ነኝ…ነገ ጥዋት ወደከተማ እንደተመለስን አሁን ለአንቺ የነገርኩሽን ጠቅላላ ቃሌን ሰጥቼ ፍርዴን እቀበላለው..በወላጆቼና በሌሎች ሰዎች ላይ የያዝሽውን ቂም ግን በቃ አዚህ ላይ አቁሚ፡፡››አለና በረጅሙ በመተንፈስ ወደኩርሲው ተመልሶ ተቀመጠ፡፡

አለም የጂኒዬርን ኑዛዜ በጥሞና ነው ያዳመጠችው….አንድም ቃል አላሳለፈችም…. እናቷ እንዴት እንደሞተች አሁን በግልፅ አውቃለች….ግን አሁንም ታሪኩ ሙሉ አልሆነላትም…‹‹በምንም አይነት ወንጀለኛውማ ጂኒዬር ብቻ አይሆንም››ስትል በውስጧ አሰበች…እሷ የሆነ ነገር ከማለቷ በፊት….እናቱ ሳራ በድንገት መናገር ጀመረች፡፡
‹‹ልጄ አንተ እንዲሁ ሰበብ ሆናብህ እንጂ ሰሎሜን የገደልካት አንተ አይደለህም››አለችው፡፡
‹‹እማዬ አሁን በቃሽ …ባበቃለት ጉዳይ ላይ ምንም ለውጥ ላታመጪ አትድከሚ››

‹‹አይደለም..ሰሎሜን የገደልናለት እኔና ስርጉት ተባብረን ነው.››

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍8228😱23
ጁኒዬር ከተቀመጠበት ተነሳ፣ ወደኩማንደሩ ቀረበና እየተንዘረዘረ ማውራት ጀመር‹‹ከዛ እኔ ጅሉን አባቷ የሰራሀውን ወንጀል እንዲደብቅልህ እና ወደእስር ቤት እንዳትገባ ልጁን ማግባትና መዛመድ አለብህ ብላችሁ አስፋፈራራችሁኝና..በሰሎሜ ሞት ከደረሰብኝ ሀዘን እንኳን በቅጡ ሳላገግም አግለብልባችሁ ስርጉትን እንዳገባት አደረጋችሁ››ብሎ አፈጠጠበት፡፡
ኩማንደሩ አንገቱን ከማቀርቀር ውጭ ምንም አልመለሰለትም፡፡

‹‹ምን አይነት ጅል ኖሬያለው…አባቴና የልብ ጓደኛዬ እድሜዬን ሙሉ እንደጅል ሲጫወቱብኝ የማላውቅ ሞኝ ››ተንሰቅስቆ አለቀሰ…እናትዬው ከተቀመጠችበት ተነሳችና አቅፋ እያባበለች ወደመቀመጫው መለሰችው፡፡

ከተወሰነ የውጥረት ዝምታ በኃላ‹‹አንድ የመጨረሻ ነገር አለ…››አለ አቶ ፍሰሀ፡፡ የሁሉም አይኖች ወደእሱ ዞረ..

‹‹ከዚህ በላይ ምን ቀረ? አለቀ እኮ… ለመስማት ሳልመው የነበረውን ነገር ሁሉ በዝርዝር አስረዳችሁኝ፡፡››

‹‹ይሄንን ለሁላችሁም ነው የምናገረው..ልጄ ጁኒዬር በዛን ቀን እናትህንና ስርጉትን ሸኝተህ ስትመጣ  ከሰሎሜ  ጋር  ስናወራ  እና  ስንጨቃጨቅ  የነበረው.  ልጄን  አታገቢውማ
..አገባዋለው በሚለው ጉዳይ አይደለም››

‹‹እና ታዲያ በምንድነው?››ጁኒዬር በመገረም ጠየቀ፡፡
‹‹ይሄንን እውነት ስነግራችሁ ሁላችሁም ከህይወታችሁ አንቅራችሁ እንደምትተፉኝ አውቃለው …ይሁን እንጂ በዚህ ለሊት እግዚያብሄር ሁለቴ ከሞት ደጃፍ አድርሶ የመለሰኝ እውነቱን ተናግሬ ንሰሀ እንድገባ ነው….ስለዚህ ነግራችኃላው…የሚያምም ቢሆን ስሙኝ፡፡አለም አንቺ የጎበና ልጅ አይደለሽም…››በቤቱ ሌላ ድንጋጤ..ተበተነ፡፡

‹‹ከዚህ በፊት ዲቃላ ነሽ አላችሁኝ ..አሁን ደግሞ ያንኑ ዲቃላነቴን ልትነጥቁኝ ነው?ይሄስ ምን ማለት ነው?››

‹‹ገመዶ ትዝ ይልህ እንደሆነ አንጃ እሷ በዛን ክረምት ለአንተም ሆነ ለማንም ሳትናገር ወደኮፈሌ ድንገት ብን ብላ ነው የሄደችው…ምክያቱም በማታውቀው ሰው ተደፍራ ነበር፡፡››

‹‹ምን? ማለት?››ዜናው ቤቱ ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉ የሚያደነዝዝ ነበር፡፡

‹‹አዎ እኛ ቤት የጁኒዬር የ19 ዓመት የልደት በዓል ዝግጅት ነበር…ትልቅ ድግስ ነበር…ወጣቶች ሲጠጡና ሲጨፍሩ ውለው ሲጨፍሩ ነበር ያመሹት…..እሷ ቤታችን እቤቷ ስለሆነ ጓዲያ ጎድጓዳውን ታውቀዋለች…ለሊት ሰባት ሰዓት አካባቢ ሁኔታው እንዴት እንደሆነ እና የለማና አየጠፋ ነገር እንዳለ ለማየት ከመኝታ ቤቴ ወጣሁና ሳሎን ሄጂ ነገሮችን ተመልክቼ ስመለስ ከእንግዳ ክፍሎች መካከል አንዱን ገርበብ ብሎ ተከፍቷል
..የሆነ ነገር ትኩረቴን ሳበውና ተጠግቼ ገፋ ሳደርገው ተከፈተ፡፡ አልጋው ላይ ከላይ ሰሎሜ ተዘርራ ተኝታ ነበር…በጣም እንደሰከረች ከሁኔታዋ ማየት ይቻላል..ቀሚሷ ወደላይ ተገልቦ ጭኗ ክፉኛ ተጋልጧል…፡፡መልሼ በራፉን ዘጋሁና ወደመኝታ ቤቴ ሄድኩ .የዛን ጊዜ ሳራ ያማት ስለነበረ ለብቻዋ ነበር የምትተኛው፡፡ከዛ የተጋለጠ ጭኖ ከህሊናዬ ሊጠፋ አልቻለም…ስጋለበጥ ከቆየው በኃላ ተመልሼ ሄድኩና ሰው በኮሪደር ላይ አለመኖሩን አረጋግጬ ወደክፍሉ ገባው፣ ከውስጥ ቀረቀርኩት መብራቱን አጠፋው… ከዛ በኃላ
ያለውን ዝርዝሩል ልነግራችሁ አልችልም…ብቻ ማን እንደደፈራት ባታውቅም መደፈራን ግን አውቃ ስለነበረ በብስጭትና በእፍረት በማግስቱ ከተማውን ለቃ ወደኮፈሌ እንደሄደች ሰማው…በእውነቱ ከፊቴ ዞር ስላለች እፎይ ነበር ያልኩት….ከሁለት ነው ከሶስት ወር በኃላ መልሳ መጣች….አሁንም ትንሽ ቆይታ መሄዷን ሳማው..ከዛ ማርገዞን እና ልታገባ መሆኑን ተወራ…ቀኑ ተጠብቆ አንቺ ተወለድሽ ..ቀኑን እስልቼ ስቆጥረው ትክክል ነበር ..የእኔ ልጅ መሆንሽን ባውቅም ለማንም መናገር የምችለው ነገር አልነበረም፡፡የዛን ቀን ልጄ ቀለበት ሊያስርላት መሆኑን ሲነግረኝ ግድ እሷን ከዛ ጋብቻ ላስቆም ብዬ የልጅሽ አባት ጎባና እንዳልሆነ ታውቂያለሽ አይደል?››ስላት

‹‹እኔስ አዎ እናት ስለሆንኩ አውቃለው..አንተ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?›› አለችኝ፡፡

‹‹እኔም አባት ስለሆንኩ ነው ላውቅ የቻልኩት ብዬ ታሪኩን በዝርዝር ስነግራት አበደች…በዛ እየተጨቃጨቅን እያለ ጁኒዬር ተመልሶ መጣ ..እንግዲህ ከጠጣችው መርዝ ጋር ከእኔ የሰማችው ዜና ምን ያህል አእምሮዋን እንደሚያስታት መገመት ቀላል ነው…እና እዚህ ዋናው ወንጀለኛ እኔ ነኝ…››

‹‹እና አንተ ..አባቴ…››አለም በተጎተተ ቃላት ከአደበቷ በግድ አወጣች፡፡

‹‹አዎ እኔ አባትሽ….ይሄንንም አሁን ወደእዚህ ከመጣሽ በኃላ በሚስጥር ሳታውቂ እኛ ቤት መጥተሸ የጠጣሽበትን ብርጭቆ በመውሰድ ዲኤንኤ በማሰራት አረጋግጬለው፡፡ እና…››ብሎ ሊቀጥል ሲል አለም ዥው ብላ በተቀመጠችበት እራሷን ስታ ወደኃላዋ ተዘረረች፡፡

‹‹ወይኔ ልጄን..አቶ ፍሰሀ ተስፈንጥሮ ስሯ ደርሶ ደገፋት….ጁኒዬር ተከተለው፡፡ገመዶ ግን ከአቶ ፍሰሀ በሰማው ነገር ደንዝዞ ሰውነቱ ሁሉ እየተንቀጠቀጠበት ነው…‹‹እጅህን ወደጎንህ ላክና ሽጉጥህን መዥረጥ አድርገህ ከአለም በስተቀር እዚህ ቤት ያሉትን ሀጥያተኞች ሁሉ ግንባር ግንባራቸውን በልና ከዛ ራስህንም ገላግለህ ለዚህች ሚስኪን ልጅ ፍትህ አስገኝላት›› የሚል ስሜት ይታናነቀው ነበር፡፡ወዲያው ከጎኑ የነበረችው ሳራ ልክ እንደአለም የሰማችውን ዜና መቋቋም አቅቷት እራሷን በመሳት ከመቀመጫዋ ተንሸራተተችና እላዩ ላይ ተዘረገፈችበት፡፡


ተፈፀመ

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
58👎27🤔11👍9🔥1
ዳግመኛ ለማናገር፣ ይቅርታ ለመጠየቅ ፊቷ መቆም ብፈልግም ፈራኋት። ሳያት የሆነ ሰው በደሌን ተነቅሶ፣ ነውሬን የሚለፍፍ ዓይነት ድብርት ይዳበለኛል። በቀን ብዛት ይሄ ስሜት ድል ይነሳል ብልም አልሆነም። ሁሌም ሳያት የሚሰማኝ ስሜት ትኩስ ድብርት ነው። እኔ ከሚሰማኝ ስሜት እሷን ስበድላት የተሰማት እና ከሚሰማት አይበልጥም ብዬ መደበቴን ታገልኩት። አንዳንድ ቀን ያበድኩት እኔ የበደለችኝ እሷ ብትሆን እያልኩ እስክመኝ ድረስ እረፍት አጣሁ። ትግሌ ከአቅሜ በላይ ሲሆን ከሃኒቾ ጋር የነበረኝን ትዝታ፣ የበደልኳትን በደል፣ ፊት መንሳቷን፣ ለማምለጥ እሷም ትዝታዋም  አይደርሱበትም ብዬ ወዳሰብኩት ቦታ ለሚስቴ አሳማኝ የሚመስል ሰበብ ደርድሬ ቤታችንን አከራይተን ያን ሰፈር ለቀን ሄድን።

በሽሽት የበዳይነት ሕመሜን ድል አደረገው ከሆነ አየዋለሁ!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢3819👍1🔥1
#ውርስ_ሕይወት

አባቴ ለብዙ ዓመታት ታስሮ ነበር። አስራ አራት ዓመቴ አካባቢ ተፈታ፤ የተወለድኩት ያን ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል፤ አባቴ ሲፈታ እኔም ተፈታሁ። አባቴ አስራ አራት ዓመት ድረስ ሳስብ የነበረውን ቀስ እያደረገ ዳመጠው።

አባቴ የላላ፣ የተቆጠበ ማኅበራዊ ግንኙነት ያለው፣ ረጋ፣ ጀንተል፣ ኮስተር ያለ ግለሰብ ነው። ብዙ ሰዓት ዝም ይላል፤ የስሜት መለዋወጥ አይታይበትም፤ ጺሙ በብዙ ሲያድግ በመቀስ በትንሹ ይከረክመዋል፤ ልብሶቹ፣ የሚጠቀምባቸው እቃዎች ስትር ያሉ ናቸው።

ከእስር እንደተፈታ እኖር ከነበረበት ከእናቴ ቤተሰቦች ቤት ወስዶ ተከራይቶ ከነበረው ሰፊ ግቢ ውስጥ መኖር ጀመርን።

ቤታችን ቅዝቅዝ ያለ ነው። ቅዝቅዝ ያለው ብዙ ወንድም እና እህት ስለሌለን ነው ወይስ እናት ስለሌለኝ ነው፣ አልያም ደግሞ አባቴ ከሰው ጋ በደማቁ ስለማይግባባ፤ ምክንያቱን እርግጠኛ ባልሆንም ውጤቱ ግን ቀዝቃዛ ሰፊ ትልቅ ግቢ ውስጥ ነው የኖርነው።

መቀዝቀዙ የገባኝ፣ በየአገጣሚ የትምርት ቤት ጓደኞቼ ጋ ቤታቸው ስሄድ ይሳሳቃሉ፣ ይጨቃጨቃሉ፣ ይካሰሳሉ፤ በዚህም እቀና ነበር። እጦታችን ያወቅነው ዕለት ጉድለት ይሰማን የለ?!

ስሜ ዋሲሁን ቢሆንም አባቴ ዋሴ ነው የሚለኝ፤ ምንም ነገር ሲያስደርገኝ ሆነ ሳደርግ አምኜበት እንዲሆን አድርጎ ሠርቶኛል። ከፍቶኝ ለምቦጬን ከዘረገፍኩ "ዋሴ ማኩረፍ የአቅመቢስነት ማሳያ ነው፤ መጀመርያ የከፋህን፣ ቅር ያለህን በእርጋታ አስረዳ" እያለ የውይይት ባሕል ልቤ ውስጥ እያኖረ ነው ያሳደገኝ።ያምንብኛል። እንደመታመን አበርቺ እጽ እንደሌለ ያወቅኩት ለራሴ ያለኝ በጎ እና የእችላለሁ ወኔ ከብዙ አቻዎቼ መለየቱን እና ምንጩን ስረዳ እና ሲገባኝ ነው።

በጨዋታ መሀል

“ይሄውልህ ዋሴ ሁልጊዜ እሮሮ የሚዘበዝቡ፣ ሁልጊዜ ሰው ማጣጣል ላይ የተመሰጡ ሰዎች፣ ሁልጊዜም አልተሳካልን ዓይነት ደረት የሚመቱ፤ ለውድቀታቸው ሰው የሚወቅሱ ሰዎች፣ ለመውደቃቸው ኃላፊነት ከማይወስዱ ጋ አትወዳጅ" ይላል።

ይሄ ሰውዬ ጓደኛ የሌለው ለውድቀታቸው ኃላፊነት የሚወስዱ አጥቶ ይሆን እላለሁ አንዳንዴ።

ደግሞ በሌላ ቀን እጅግ ብዙ ቆይቶ

“ዋሴ" ይላል። ልገልጸው የማልችለው አጠራር አለው። ሁሉም ሰው ዋሴ ብሎ ቢጠራኝም በእሱ ዓይነት መንገድ የሚጠራኝ ሰው አልገጠመኝም። የሆነ አለኝታዬ ዋስትናዬ የሚለኝ ነው የሚመስለኝ፤ እወድሃለሁ የሚለኝ በአጠራሩ ውስጥ ባለው ድምጸት በኩል ነው።

"ይሄውልህ ዋሴ ሰው አንተ ላይ ስለሚይዘው . አቋም እንዳትጨነቅ፤ ሰው ለማስደሰት ከዳከርክ የራስህ እውነት ሳይኖርህ ታልፋለህ" ይላል።

አባቴ ጥንቅቅ ያለ ሰውዬ ነው፤ ነፍስ እያወቅኩ ስሄድ ነው ለእሱ ያለኝ ፍቅር እና አክብሮት ያየለው።

ብዙ ዝም ስለሚል ሲያወራ ተስገብግቤ ነው የምሰማው፤ እጦትን የመሰለ ነገሮችን ተፈላጊ አድራጊ ያለ አይመስለኝም እኮ::

"ይሄውልህ ዋሴ"

ወዬ አባቴ

“ስንት ዓመት መቀመቅ ያወረደኝ ሐቀኝነቴ ነው፤ ኃላፊነቴን በአግባቡ ለመወጣት ስዳክር፤ ብልሹ ካልኩት አሠራር ጋ ስታገል፣ መደለያቸውን በጄ ስላላልኩ መቀመቅ ውስጥ ወረወሩኝ።

ብቻዬን ቆምኩ!

በእርግጥ እኔ ቆምኩ ልበል እንጂ ለብዙ ሰው ወድቄያለሁ፤ የወደቀ ከሚለው ጋ ማበር የሚፈልግ ማን አለ? ወደቀ ብለው ተዘባበቱብኝ፤ ስንት ዓመት ለመኖር ነው ግን እንዲህ የከፉት እላለሁ፤ ስለ ተቻለ ብቻ አሳማም ጅብም እንዴት ይኮናል?!

ይኸውልህ ዋሴ

ለእራስህ እውነተኛን መሆን የመሰለ የሕሊና እረፍት የለም፤ ከራስ ጋ ሰላም ከመሆን በላይ ምን ሽልማት አለ? ወድቋል ብለው ሲዘባበቱ እኔ ያልሠራሁት መጥፎ ተግባር ምቹ ትራስ ሆኖኝ ከሰላሜ ጋ ነበርኩ።

አንተ እንዲህ የምትወደኝ እኮ፣ አንተ እንዲህ የጎበዝክልኝ'ኮ ለእውነቴ የተሰጠኝ ሽልማት ነው፤ በዚህ ዕድሜ ጤነኛ የሆንኩት እኮ አምላክ ለመታመኔ የሰጠኝ ስጦታ ነው፤ ሰው ሽልማት ጥሬ ገንዘብ ብቻ ይመስለዋል" ይል'ና በስሱ እንደሁሌው ጥርሱን ገለጥ አድርጎ ፈገግ ይላል፤ አሳሳቁ ሞገስ አለው!!

“እኔን ያሳቀሉኝ እኮ በእስተርጅና የሚመታቸው ልጅ፣ የማይወዳቸው ልጅ ኖሯቸዋል፤ ያመኑት ክዷቸዋል፡፡

“እግዚሃር በሚደግሱት ዝክር የሚሸወድ መስሏቸዋል" እያለ አፉን በትንሹ ከፍቶ ጥርሱን እያሳየኝ ፈገግ ይላል።

አባቴ የሚለኝን ሁሉ እየሆነ ያሳየኝ መምህሬ ነው።

“ይኸውልህ ዋሴ ጥቃቅን ነገር ላይ አታተኩር፤ የምትኖርለት መርሕ ይኑርህ፤ እመቀመቅ ድረስ የምትሄድለት ሕልም እና መርሕ ይኑርህ።"

የሚኖርን እውነት ከመስማት በላይ ምን ሐሴት አለ??

ብቻዬን መቆም አስተምሮኝ፣ ጥቂት ቀን ታሞ ጥቂት ቀን አስታምሜው አለፈ። ብዙ ቆይቼ እስር ቤት ሳለ የጻፋቸውን ሐሳቦችን እና ገጠመኞቹን ሳነብ ከዕድሜዬ በላይ አበሰለኝ።

ሕይወቴ ላይ የብስለቱ ዳና ያረፈብኝ የአባቴ ልጅ እኔ ዋሴ ነኝ!!!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
47👏18
#ሊያብብ_ሲል

ሱስ ሳይበላው፣ ሲጋራ መግዣ መለመን ሳይጀምር፤ ጉስቁልና ሳያፈዘው፤ ለልብሱ መቆሸሽ ደንታ ቢስ ከመሆኑ በፊት፤ ሰዎችም ሲጣራ ባልሰማ መሄድ ሳይጀምሩ፤ ቃል አባይ ከመሆኑ በፊት፤ ክብሬ ማለት ሳያቆም፤ ለትንሽ ለትልቁ መላክ ሳይጀምር በፊት… ቆንጆ፣ ተወዳጅ፣ ዘናጭ ነበር። ከጓደኞቹ በላይ ድምቅ ያለ ልጅ ነበር፤ ቆንጆ አማርጦ ይሰክስ ነበር፤ የጸጉሩን ፍሪዝ በመሰታወት አስር ጊዜ እያየ አስር ጊዜ ያስተካክል ነበር።

ሕልመኛ ነበር። እንደ ሁሉም ወጣት ሀብታም መሆን፤ አዋቂ መሆን፤ ቤተሰቦቹን የመርዳት ሕልም ነበረው። የተንሸዋረረ አራድነት አሳስቶት የለኮሳት ሲጋራ፤ ለሳቅ ብሎ የተጎነጫት አረቄ፣ ለሙድ ብሎ የቀነጠሳት የጫት ቅጠል ስትደጋገም አፈዘዘችው፤ ሕልሙን ወጣትነቱን ክብሩን አረገፈችው።

ማንም ብርቱ ነኝ ቢል ታግሎ የማያስመልሳትን ወጣትነቱን ለማያቀው ጣዖት እየሰዋት ነው።

ጥግ ላይ ተቀምጦ ዘመን ሂዶ ዘመን ፤ በመጣ ቁጥር የሚመጡ ለውጦችን ከዳር በትዝብት እየተመለከተ ጊዜው እንዴት ነው የሚሮጠው? የሚል ይመስለኛል።

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
14👍5🔥3
#ባል_ተመኘሁ

አስተዳደጌ ነው የገደለኝ። አስተዳደጌ መጠበቅ እና ማግኘት ነበረበት። አባቴ ሁሌ ቃል ይገባልኛል፣ የሆነ ነገር በጥሩ መልኩ ሳደርግ ይሸልመኛል፣ እናቴ የቤት ሥራ ስሠራ ታመሰግነኛለች፣ ትመርቀኛለች። በምስጋና እና በስጦታ ተንበሽብሼ ነው ያደግኩት፤ ለዛ ነው የጠበቅኩትን ሳጣ የምታመመው ብዬ ሁላ አውቃለሁ፤ ግን በእሱ ብቻም አይደለም!

የማያቸው ሮማንቲክ ፊልሞች እና የማነባቸው መጻሕፍት ናቸው፤ ከፍቅር የሚገኘውን ደስታ እና ሁኔታ ከሚገባው በላይ አጋነው፣ ከቅዱስ የማገኘውን ነገር ሁሉ ያሳነሱብኝ ብዬም አምኜ አውቃለሁ።

ግን እሱ ብቻ አይደለም!

ቅዱስ ራሱ ነው ፍቅረኛሞች እያለን አባቴን መስሎ እና ሆኖ ተንከባክቦ ኑሮ ስንጀምር እርግፍ አድርጎ ትቶኝ የተፈላጊነት ስሜቴን የገደለው።

ኖ በእሱ ብቻም አይደለም!

ገመናዬን፣ ሚስጥሬን፣ ስሜቴን ለሰው ስለማልናገር ነው መፍትሔ ያጣሁት፤ የማይቀለኝ! የሚያብከነክነኝ!

ግን ዋናው ምክንያት ይሄም አይደለም!

ራሴን ከዋናው የሕመሜ ምክንያት፣ የድባቴዬን ምንጭ ለራሴ አልነግር ብዬ ነው።

ቅዱስ አይፈልገኝም። ሲመጣ ባዶ ቤት ቢቆየው ቅር አይለውም። ለስሜቴ ደንታ የለውም። ቆይ ስንት ወራቶች ሞላን ወሲብ እንኳን ከፈጸምን? አልጋ ከለየን ስንት ጊዜ ሆነን? ስንቴ ተዘገጃጅቼ ሊወጣ ሲል፣ ሲገባም ላነሳሳው በሚል አጋጣሚ አስመስዬ ራቁቴን የታየሁት፣ ቀስቃሽ አለባበስ ስንቴ ነው የለበስኩት?

እሱ ግን አያየኝም።

እንዲያዝንልኝ ታመምኩ፤ ኡኡ ነደድኩ፣ ጠዘጠዘኝ፣ ወጋኝ አልኩ፤ ታከሚ ይላል እንጂ አይደነግጥም። ወጣ ብሎ ስልክ ረጅም ሰዓት ያወራል።

መሀላችን ያለው ችግር ቀላል ነው ብዬ አስመሰልኩ... እውነቱ ግን እሱ አይወደኝም።

በመጨረሻ አልፈለግነት ሲጫወትብኝ፣ የድሮ ቦይፍሬንዴ ጋ ሄጄ ተልከሰከስኩ!

እሰይ!! እንኳን ተልከሰከስኩ።

ለሴት ልጅ የአለመፈለግነት ስሜት፣ ለዛውም በእንክብካቤ ላደገች፤ ለዛውም ተለማምጦ፣ ልዕልቴ ናት ብሎ ላገባት፣ ለዛውም መፈለግ እና መውደድ ለምታውቅ ሴት የሚሰማትን የሕመም ስሜት የት ያውቀዋል?!

የምን ጉዝጓዝ፣ ሰበብ፣ ድሪቶ፣ ዝባዝንኬ ነው?!

አለመፈለግ ብቻውን ቀላል ነው?!

ብቻውን ትዳርን መፍታት ብቻ አማራጭ አድርጎ ማሰብ ቀላል ነው?

ብቻውን ወሲብ ማድረግ መፈለግ እና ባል እያለ በፍትወት መቸንከር ቀላል ነው?

ብቻውን ላወራው እየፈለግኩ፣ ስደውልለት ሳያነሳልኝ ሲቀር አያከብረኝም፣ ከምንም አይቆጥረኝም ዓይነት ስሜትስ ቀላል ነው?!

ብቻውን እንዲህ እለዋለሁ ብዬ የሰበሰብኩትን ዓረፍተ ነገር፣ እንዲያዝንልኝ ያጠናሁትን ንግግር፣ እንዲታረቀኝ ያጠራቀምኩትን ቃላት፣ እንዲሳሳልኝ ያከማቸሁትን ሰበብ፣ እንዲረዳኝ የተዘጋጀሁበትን ቃል ፊት ነስቶ ሲያጠፋብኝ ስሜቱ ልብ አይሰብርም??!

ከድሮ ቦይፍሬንዴ ጋር ተንገብግበን፣ ተጠማጥመን ተዋሰብን። ቆንጆ ነኝ ወይ ስለው "ከድሮ በበለጠ” እያለኝ፤ ምኔን ትወድልኛለህ ስለው እያንዳንዱ አካሌን . እየሳመ እያሳየኝ። እየተዟዟርን፣ ቦታ እያማረጥን ተዋሰብን።

ደስስስ አለኝ!!

ለመለምኩ! እየጠወለግኩኝ ነበር።

ያደረግኩት ተግባር ለሌላው፣ ለመንገደኛው፣ ለመርሕ ሰው ሁሉ፣ ለጨዋው ሁሉ፣ ለአማኙ ሁሉ፣ ከዳር ሆኖ ላየኝ ሁሉ፣ ለፈራጅ ሁሉ፣ ለሌባው ሳይቀር ዝሙት ነው!.

ወሲብ ውስጥ ያለውን እፈልግሻለሁ፣ ታምሪያለሽ፣ እወድሻለሁ ሽንገላን መስማት ናፍቆኝ ነበር።

አመሰግንሃለሁ ብዬ አንገቱ ውስጥ ተወሽቄ ሳምኩት። ስለተኛኸኝ አመሰግናለሁ ይባላል? ትዳሬ ላይ ከባለግኩኝ በኋላ ማመስገን ነበረብኝ?

እኔ ግን አመሰገንኩት!

ተሰናብቼው ሳይመሽብኝ ወደ ቤቴ ፈጠን ፈጠን እያልኩ መሄድ ጀመርኩ፤ ቀስ እያልኩ ፍጥነቴን ቀነስኩ፤ እዛ ዱካክ፣ አልፈለግነት የሚበላኝ ቤት መሄድ ፈራሁ። የማይፈልገኝን ባሌን ማየት ሲዖልን የማየት ዓይነት ሆነብኝ፣ የማይናፍቀኝን፣ የማይንከባከበኝ ባሌ ያለበት ቤት መሄድ ጠላሁ፣ ወስልቼበት እንኳን ጸጸት ያልተሰማኝ ባሌ ጋ መሄድ አስጠላኝ።

ለመጀመርያ ጊዜ ልቤን ሰማሁት።

ከእኔ ካልሆነ ሰው ጋር እንድተኛ ያደረገኝ ሰውዬ ጋ ምን አደርጋለሁ??

መሳም እስክናፍቅ ድረስ የገፋኝን፣ መታቀፍን ብርቅ ያደረገብኝን፣ መወደድ እንደሚገባኝ ያሰረሳኝ ሰው ጋ ምን አደርጋለሁ?!

ምን አጠፋሁ? ይቅርታ ለማለት፣ ምን ላድርግልህ እንድለው ትንሽዬ እንኳን ፊት የማይሰጠኝ ሰው ጋ ለመኖር ለምን ወደኋላ ተመለስኩ።

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
36👍4😢1
#ምሶሶ_እና_ማገር

ሸክሜን ሳላስተያየው፣ ፍላጎቴን ቸል እያልኩ ከኔ በቀር ማን አለው ለምለው ቤተሰቤ ስል ፍላጎቴን አቀዝቅዤ መናገር የምፈለገውን ሁሉ ሳልናገር እንደ ጓደኞቼ ፋሽን ልከትል ሳልል ኑሮን ለማሸነፍ ስለምባትል ...

የቤታችን ምሶሶ እኔ ነኝ ባይ ነበረኩ!!

ድንገት እናቴ በአስር ቀን ሕመም ተለየችን። ቤታችን በፍጥነት ቀዘቀዘ።

እናታችን የአባቴን ስኳር፣ ደምብዛት እና ኮሌስትሮሉን ያማከለ ምግብ አቀናብራ አቅራቢ ነበረች። ተኝቶ ሳለ ከውጪ ሆነ ከቤት ውስጥ የሚረብሽ የመሰላት ድምጽ ከተተነፈሰ ቀስስ ቀስ ገረመው ተኝቷል ትላለች ድምጿን ለምልክት በቀረበ ማንሻካሾክ። አባታችንም እንዳይረበሽ ድምጽ ቀንስ ለምትለውም ሰው እንዳይቀየም እየተጨነቀች። አባታችን እናታችን ከሌለች ቤት ውስጥ ያገኘውን ሰው 'አልሚ የት ሄዳ ነው? በቃ አንዴ ከወጣች አትመለስም?' እያለ በስሱ ይነጫነጫል። ምቾቱ ሲሰወርበት ማን ዝም ይላል?

የታናሽ ወንድሜ ሱስ ያመጣበትን ግትልትል ብልግና የምትደበቅለት፣ የምትሸሽግለት፣ ብላ እንጂ ገንዘብ የለህ እንደው አንዱ ቦታ ገባ ብለህ የምትጎርስበት፤ እነዛ ጓደኞች እንደሆኑ ሊያጠጡህ ነው የሚፈልጉህ... ደግሞ ሰውነትህ እየቀነሰ ነው... ወይ እንደ ጎረምሳ ጎረስ ጎረስ አድርገህ አትበላ፣ በየትኛው አንጀትህ መጠጡን እንደምትችለው... እያለች ሳትሰለች ግሳጼ እና ምክር እያቀላቀለች ትኩረቷን የማትነግፈው፣  የምትቆረቆርለት፣ ከብልግናው መሀል መልካምነትን አነፍንፋ የምትመሰክርለት እሷ ብቻ ናት።

“ምዕራፌ እኛን እኛን እያልሽ ራስሽን አየበደልሽ እኮ ነው። ጸጉርሽን ተሰሪ እንጂ ደግሞ አማረልኝ እያልሽ ትጎምጂው እና ትጣይኛለሸ! ሴት ልጅ ጸጉሯ ነው ውበቷ..."

ውጪ ስትንገላታ ነው የምትውለው እያለች ታቀብጠኛለች፣ ትመክረኛለች፣ ገመናዬን ትሰማኛለች፣ ትገስጸኛለች፣ ጠዋት ማታ መግባት እና መውጣቴን፣ ሁኔታዬን፣” ገጼን፣ እንቅስሰቃሴን ትከታተላለች።

አደራህን ጌታዬ ከልጆቼ በፊት አድረገኝ፣ የልጅ ሐዘን አታሳየኝ፤ ከጓደኛ በታች አታውላቸው፣ ከክፉ ነገር ጋርዳቸው፤ ለኔ ያደረከውን ለማን አደረክ? ተመስገን፤ ተመስገን አያለች ስታጉተመትም ለሚሰማት ከአምላኳ ጋር የምታወራ አትመስልም፤ ከወዳጇ ጋር እንጂ!! በርግጥ ለታመነ ካምላክ በላይ ወዳጅ ማን አለ!

ምዕራፌ በርቺልን፣ ካላንቺ ማን አለን? አያለች መኖርያ ምክንያት ትለግሰኛለች። ለመመረቅ ሽራፊ. ምክንያት የምትፈልግ ይመስል ላደረኩት ትንሽ ነገር  ስትመርቀኝ ትውላለች።

ለውሻችን ቦቸራ እንኳን በሰዓቱ ምግብ የምትወረውርለት፤ አሞታል እንዴ? ፈዘዘሳ ብላ የምታስተውለው እናቴ ብቻ ናት።

ዘመዶቻችን እንዲመጡ ወትዋች፣ ጠፋችሁ ብላ ወቃሽ፤ ሲመጡ ተንከባካቢ፤ ካልበላችሁ፣ ካልጨመራችሁ፣ ካልቆያችሁ፣ ካላደራችሁ እያለች የምትለማመጥ፤ ሰፈራችን ውስጥ ለቅሶ ሲኖር፣ ሰርግ ሲሰረግ፣ ዝክር ሲዘከር ግንባር ቀደም አጋዥና አድማቂ እናታችን ናት። ለሚውል መዋል፣ ለደግ ደግ መሆን ስለማይከብድ ቤታችን ጉዳይ ሲኖር የሚያግዘን፣ ስንታመም የሚጠይቀን፣ መንገድ ላይ ሰላምተኛችን ብዙ ነው።

ስናጣት ልካችን ተገለጠልን!! እንዴት ይሄን ሁሉ ስትሸከም በዚህ መጠን  አላስተዋልኳትም? ተሸክሞ ሸክምን አለማሳየት ምን ዓይነት ጥበብ ነው?? እናቴን ያሳረፍኳት መስሎኝ ነበር፤ ለካ አሳርፋኝ ነው።

እናቴ ስንት ቀን ፍቅሯ እውነቷን ሲያስደብቃት፤ በድዬ ለእኔ ስታደላ አይቻታለሁ። ልጅ ሳለሁ በንዴት ከገረፈችኝ በኋላ ሲቃ እየተናነቀኝ ጉያዋ ስወሸቅ፣ ተንሰፍስፋ ያባበለችኝ ዕለት ትውስታ ልቤ ውስጥ አለ።

ድከመቴን የማታጎላብኝ፤ መውደዷ · የማይወላውል፣ እንደምወዳት ማስረጃ የማታስስ፤ ተዝረክርኬ ዝንጥ እንዳልኩ የምታሰማኝ፤ ሕመሜ የሚያማት፤ ስኬቴ ከሁሉ በላይ የሚያስፈነድቃት፣ ነገሬን ሁሉ ጉዳዬ ነው የምትል፤ እንደምወደድ እስትንፋሴ ዓለም ላይ ካረፈ ጀምሮ እያሳየች

የመሰከረችልኝ። እምወደድ እንደሆንኩ ልቤ ላይዐያሰረጸችልኝ፤ መወደድን የሚያክል ምንም በረከት እንደሌለ በምርቃት እና በጸሎቷ ያሰማችኝ።

ጥንካሬዋን ፈተና የማይበግረው፣ በደል ሆነ መከፋት የማይሽረሽረው፤ ትሕትና የተላበሰች፣ በየቀኑ ስለ ልጇ ከአምላኳ ጋ የምታወራ  አመስጋኝ፣ ስጉ : ፍጥረት : ናት። እስክንጠግብ የማይርባት፤ አሟት በድካም የምታሳብብ፤ እየረገመችን የምትጸልይልን፣ አንደበቷ ከእውነቷ ጋ የማይገጣጠም ድብቅ ፍጡር ናት። ፍላጎቷን አሽሻ፣ የምትፈልገውን አጣጥላ ለምንወድው ነገር ፍላጎቷን የሰዋች፣ ለልጆቿ ቸር፣ ለራሷ ስስታም ናት።

የልጇን ፊት እንደ ዳዊት ዘወትር የምታነብ፤  ስትናፍቅ፣ ስናረፍድ በስጋት የምትቃዥ እናት፤ የፍጡር ፍቅር ጥግ ናት።

ዋርካችን ሲገነደስ የከለለልን ገበና ገለጠን!

ሞቷ ከእንባ በላይ ነው። አልቅሼ ላውጣው ብል አይወጣም። አንዳንድ ጊዜ አጠገቤ ያለች ይመስለኛል፤ ባትመልስልኝም የልቤን እንዲህ እያልኩ አወራታለሁ።

ለምን የሚወዱሽ ሲያለቅሱ፣ ደረታቸው ሲደቁ፣ ጸጉራቸውን ሲነጩ ዝም ብዬ ፈዝዤ ተመለከትኳቸው?  አቅፈውኝ፣ አዝነውልኝ፣ እያለቀሱ ሲያባብሉኝ ለምን ደነዘዝኩኝ?
ግድ የለም አብሬሽ ሞቼ ነው የሚሆነው። አብሬሽ ሞቼ ባይሆን ድንኳኑ ውስጥ ወዳጅ አዝማድ ተስብስቦ ሲጨዋወት፣ ሲያጽናና እኔ ለምን ብቻዬን ዲዳ ሆንኩኝ?

አብሬሽ ሞቼ ባይሆን

የሚቀርበኝ ጉድሽ ፈላ እያለ ሲመለከተኝ፤ በርቺ አይዞሽ እያለ ማጽናኛ የቃላት ጋጋታ ሲያንጋጋ እንዴት በዚህ ሁሉ መሀል የእንባ ቋቴ አልተረታም? ከሩቅ፣ ከቅርብ ቀዬ ሐዘኔን በአካል ሊጋሩኝ መጥተው አይኔን እያዩ ሲያጨዋውቱኝ፤ ሊያበረቱኝ ሲታገሉ እንዴት ሆድ አይብሰኝም?

አብሬሽ ሞቼ ባይሆን

ቆሌ፣ ቅስሜ፣ ደመነፍሴ፣ ትውስታዬ፣ መጓጓቴ፣ ሕልሜ አብሮ ከአንቺ ጋ ባይቀበር እንዳሁኑ መች እሆን ነበር?

ከዚህ በኋላ አለመኖርሽ አንዴት አያባባኝም?

አንቺ ሞተሽ እኔ አብሬሽ ሞቼ ባይሆን አንድ ዘለላ እንባ እንዴት አልወጣኝም?

ይሁን ሁሉም... አብሬሽ ሞቼ ባይሆን ለምን ምሳዬ አይርበኝም? እንደሁሌው ውሃ ጥሜ ለምን አይታወቀኝም? ቆይ እሺ ለምን አትናፍቂኝም? አብሬሽ ሞቼ ባይሆን፣ ዋርካዬ ሲገነደስ እንዴት ዝም እላለሁ?

ነገሩ ምሰሶው ሲወድቅ ነው ማገር ማንነቱን የሚያውቀው።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
22😢16👍1
“ምድር ከሰጠችኝ ገጸ በረከት እሷ ዋነኛዋ ነች። ምድር ላይ መቆየት ካማረኝ የሚያምረኝ በእሷ ምክንያት ነው። የሕይወት ተጋድሎዬን ያህል ነው ትርጉም የምትሰጠኝ፤ በዚህ በዝባዥ ስርዓት፣ በእዚህ አምባገነን ስርዓት፤ ሕዝብ ከቁጥር በቀር ትርጉም በማይሰጠው ይህን በዝባዥ አገዛዝ እታገለው ዘንድ እሷ የምትሰጠኝ ተስፋ እና ፍቅር ግዙፍ ነው።

'Socialism እና Karl Marx' እንደማይነጣጠሉ ሁሉ የኖረኝ ክብር እና ዝና ከእሷ ከሚስቴ ጋር ሊነጣጠል እና ካለ እሷ የሚቻል አልነበረም። አይኔን አይታ የምትታዘዘኝ እና የምታዝንልኝ የእኩለ ሌሊት ብርሃኔ እሷ ናት።

እሷ ጠይም የደስታ መግቢያ በሬ ናት። እሷ ሳትኖረኝ ምንስ ቢኖረኝ ምን ያደርግልኛል? ስንት ቀን እሱን ያየ፤ ከእሱ ጋ የቆመ እንደሎጥ ሚስት የጨው ሐውልት ይሆናል ተብሎ ታውጆ እንኳን ምን ቢመጣ ካላንተ ስሆን ከሚሰማኝ አይበልጥም ብላ አብራኝ ነበረች፤ ስንቴስ መቀመቅ ሲያወርዱኝ ከእሷ በቀር ማን አብሮኝ ቆመ?

እሷ የነፍስ ምግብ ጸዳሌ ናት። ምንም ብሆን፤ ምንም ባጣ የማይደንቀኝ ልበ ደንዳና እንደሆንኩ ያለፍኩበት ጨለማ ይመሰክራል፤ እሷ ብቻ ከእኔ ጋ ትሁንልኝ እንጂ።

እሷ ከቀደመችብኝ ያን ዕለት ነው ኩራባቸው መንፈሱ የሚታወከው፤ እሷ ካለችማ ኩራባቸው ልቡ ላይ ሐሴት እንደተመላለሰ የተሰፈረለትን ዘመን ይጨርሳል ..

እሷ የልቤ ብርሃን ናት። ግፍን እቋቋም ዘንድ የተቸረችኝ ጫንቃዬ ናት፤ በንፅሕና ከእውነት ጋ እንድቆም፤ አቋሜ እንዳይሸረሸር፤  መንገዴን፣ አቋሜን  በፍቅር  ከመንገዴ እንዳልሰናከል በትልቁ አቅም ሆናኛለች።

በጠላት፣ በአሰናካይ፣ በቀለብተኛ ተከብቤ : ሳለሁ እንዳላፈገፍግ የምታበረታኝ የደስታዬ ፍላጽ መዓዙን የዓላማዬ ያህል ነው የምወዳት... ይላል። .

ሌላ ገጽ ገለጥኩ

'I will not quit until I make my dreams come true. tius. ኣ"ደምን እንደምን ድምጽ ለመሆን መጥቼ ዝም እላለሁ?

በዜጎች መሀል ግጭትን የሚቸረችር አገዛዝ፤ የማንነታችንን ግንብ የሚሸረሸር ትርክት  የሚያንሸረሽሩ ቀለብተኞች ባሉበት፤ ግፍ ባራኪ፣ ሞራል አልባ አሸከር፣ ፈሪ፣ መርሕ አልባ አለቅላቂ ልሒቃን በተሰባሰቡበት ምድር ተገኝቼ  እስክሞት ዝም አልልም። ደግሞስ ላለመሞት አልመጣሁ፣ ይግደሉኝ እንጂ መቼም እንደማልደለል እኔም፣ መዓዙም፣ እነሱም ያውቃሉ።

እኔ ኩራባቸው ዓለሙ አገር እንድታብብ ከማለም በቀር፤ መነሻ አልባ ትርክት ከማጋለጥ በቀር አንድም ስውር ሕልም እና ግብ ኖሮኝ እንደማያውቅ የልቤን እውነት የምታውቀው መዓዚ እና ሕያው አምላኬ ምስክር ነው እንጂማ ስንቴ በስልጣን ሊደልሉኝ ታከውኝ የለ! እንጂማ በጉቦ ሊጥሉኝስ አላሴሩም? እኔ ኩራባቸው ሳንቲም ግድ የሚሰጠኝ መስሏቸው… ሃሃሃሃሃ የሚታገሉትን ኩራባቸውን አያውቁትም ::

ሌላ ገጽ ገለጥኩ

“አንቺ ግዙፍ ሕልሜን የምታክይ፤ አይበገሬው ልቤን የበገርሽ፣ ኮስታራ ግንባሬን ገንብረሽ ለፈገግታ የራቀውን ፊቴን የምታፈኪ ሚስቴ ሆይ የሕይወት ዘመን ንዑዴ ነሽ። በትንሽ ቀልድ፣ በትንሽ ጨዋታ የምትደሰችልኝ፤ በወደኩበት
በታመምኩበት በታሰርኩበት ሰው ሁሉ ፈርቶ ከእኔ ሲርቅ፣ ከእኔ ጋ ላለመተያየት ሲደበቀኝ በኩራት ፈቅደሽ መርጠሽ ከእኔ ጋ የሆንሽ የእኔ መዓዚ ሕልሜን ልቤ ውስጥ ካስቀመጠው በረከቴ እኩል ባንቺም ተባርኬያለሁ። ባንቺ ምክንያት የምድር ቆይታዬ ከሕልሜ ያላስበለጥኩት የእኔን ያህል መርሄን ስለምትወጅልኝ መስሎኝ...

ጽሑፎቹ እንኳን ለጉዳዩ ባለቤት ለማንም መንገደኛ ትርጉም ይሰጣሉ፤ አጀንዳውን ከተቀመጠበት አኖርኩት፡፡

ጋሼ ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ፣ መንግሥት እንቅስቃሴውን የሚያጠናው፣ መንግሥትም ሆነ መንግሥት የሚቃወሙ አካላት በዛቻ እና በንዋይ ሊደልሉት እንደሚሞክሩ በርካታ ጸሐፊያን በማስረጃ ከትበው አንብቤያለሁ፡፡ እንዲህ እየወደዳት፣ እንዲህ እየተመካባት፣ እንዲህ እየተንሰፈሰፈላት ሲቀጭባት፣ ሜዳ ላይ ሲሞትባት የገዳዩን ማንነት ከመላምት በቀር ገላጭ ሲጠፋ አረቄ ውስጥ ባትደበቅ ከማዘን ውጪ ማጠንከሪያ አቅም እና ሞራል ከየት በኩል ይወለዳል?

ብዙ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ሰዎች ስለ ኩራባቸው ዓለሙ ቃለ መጠይቅ እንድትሰጥ ይለምኗታል። አንድም ቀን ግን እሽ ብላ አታውቅም። አንድ ዕለት ስለ ሌላ የባጥ የቆጡን እያወራሁ ሳለ ...

እኔ የምልሽ አታቲ ለምንድን ነው ግን ስለ ጋሼ ምስክርነት፣ እውነት እና የሕይወት ዘመን እንቅስቃሴው የማትናገሪው? ካንቺ በቀርስ ስለሱ ሊያወራ የሚችል ማን ይኖራል? አልኳት...

አታቲ አይኗን ቦዘዝ አድርጋ ጠረጴዛው ላይ ከተቀመጠው ትልቅ ጉርድ ፎቶ ላይ በትካዜ ተክላ

“ይሄውልሽ ዕድሌ ኩራባቸው ምስክርነት አያስፈልገውም። የራሱን ሐውልት ገንብቶ ነው ያለፈው፤ ስለ እሱ ከሥራዎቹ በላይ መናገር የሚቻለው አንድም የለም። ሥራዎቹን መመርመር እና ሥራዎቹን መሞገት ይችላሉ፤ ሕልሙን ጽፎ
አቋሙን ተንትኖ ታግሎ የተሰዋ ሕያው ነው፡፡ ከጻፈው ውጭ የምናገረው፣ ማለት ፈልጎ ያላለው አንድም እውነት የለውም። ከእኔ ጋ ያሳለፍነውን በየሜዳው፣ በየስፍራው ለማንም አላወራም፤ ይነፍስበታል፣ ይቀልብኛል፤ ቀስ እያልኩ እየተረኩ እያዋዛው፣ እያስታወስኩ ራሴ ጋ የማስቀምጠው የሕይወት ዶሴዬ ነው..."

አታቲ ትንሽ ስትቀማምስ ጀግና እንዳላገባ የምትመክረኝ ምክሯ አልሠራም። ከቢልልኝ ጋ ተፋቀርን፤ ቢልልኝ እውነት፣ ከስሜትም፣  ከፍቅርም ይበልጣል የሚል የዘመኑ የማይናወጥ ጀግና ነው።

አታቲ ሞቅ ባላት ቁጥር “ጀግና እንዳትወጂ” ብትለኝም ልቤ ግን ጀግና፣ ባለ ራዕይ፣ ትጉህ እያየ ስላደገ ጀግና ከማፍቀር የታደገው የለም።

ቢልልኝ ኩራባቸው ዓለሙ አሳዳጊ አባቴ እንደሆነ ሲያውቅ የተሰማው ሐሴት ልዩ ነበር። የሰው ማንነት፣ እውነት የተወሸቀው እያየ ባደገው የተበጃጀ ፍጡር ነው ስለሚል የደስታው ምክንያት አልጠፋኝም።

ቢልልኝን አንድ አርብ ዕለት አመሻሽ ላይ ከአታቲ ጋር አስተዋወቅኳቸው። በጋራ እየተጫወትን ሳለ ጨዋታችን ሀገር፤ ትግል፤ እውነት፤ ታሪክ ሆነ። አታቲ የቢልልኝ ሐተታ ምቾት የሰጣት አልመሰለኝም። ስትሰማው ቆየች እና ተቆርቆሪነትህ እና አቋምህ ዋጋ እንደሚያስከፍል ታውቃለህ አይደል? አለችው በፍጹም እናትነት በስስት እያየችው።

ቢልልኝ ትንሽ ዝም ካለ በኋላ እኔ እንደምጠራት “አታቲ" አላት ፊቷ ሐዘን እንደተላበሰ በቀጥልልኝ ዓይነት አየችው
"ክብር አይደለምን ለሚያማኑበት ጉዳይ ዋጋ መክፈል?” ኣላት። ትክዝ ብላ እኔንም እሱንም አፈራርቃ ካየችን በኋላ አቅም አልባነት ፊት እያሳየችን መርዶ እንደሰማ ሰው በእንባ ታጅባ “አዬ መረገሜ” አለች፡፡

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
38
#እንባ_አዳሽ_ነፍሶች

አብረውኝ ከሚሰሩት ለየት ይልብኛል፤ ግሬይ፣ አመድማ፣ ሽሮ ከለር ልብሶች ያዘወትራል። አይዘንጥም፣ ጸጉሩን ስለማይንከባከብ የብርድልብስ ብናኝ በተለይ ጠዋት ላይ ከጸጉሩ አይጠፋም። ጺሙን በቶሎ አያነሳውም፣ ከሰው ጋ አይተራረብም፣ ሰው ሲተረብም አይስቅም። ፖለቲካ ይከታተላል፣ አንባቢ ነው፤ ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅን ይወደዋል፤ ጆን ሎክን ይተነትናል፤ አረቄ ነፍሱ ነው።

አንዳንድ ጠዋት የተመሳቀለ ፊት ይዞ ይመጣል። ፊቱ አልኮል ያመሳቀለው ይመስለኛል። ስለ ራሱ አያብራራም፣ ሰው እሱ ላይ ሰለሚይዘው አቋም አይጨንቀውም።

የሚረዳው የለም ብዬ ዋስ ጠበቃ ለመሆን እጋጋጣለሁ፣ ግን ነገሮችን ስለሚመረምር ለራሱ አያንስም።

ሲያወራ፣ ሲሰማ፣ ሐሳብ ሲሰጥ ጥድፍ ጥድፍ አይልም። የዋዛ አንቅስቃሴዎቹ ላይ እንኳን እመለከታለሁ። አስተውሎትን

ሰኞ ዕለት ያሳደገው፣ ያስተማረው አንድ ወንድሙ በመኪና አደጋ ሞተበት። የቢሮ ሰዎች ተሰባስበን ቀብር ላይ ተገኘን። ብሩክ ፍልስፍናው፣ መጀናተሉ ቀሰስ ማለቱ ከእሱ በኖ ጠፋ። መሬት እየተንከባለለ ሲያለቅስ ሳየው አንጀቴ ተንሰፈሰፈ። እንባዬ አካላቴን ሳላወናጭፍ፣ ድምጽ ሳላወጣ ወለል እያለ ወረደ። ብሩክ አቅም አልባነት ሲያጥመለምለው፣ ለብዙ ሰው አለኝታ የነበረውም ወንድሙ ተጀቡኖ ወደ ጉድጎድ ሲወረወር ከንቱነት በላኝ።

በነጋታው ጠዋት ከእነ ዱካኬ ከእንቅልፌ ነቃሁ። ተጣጥቤ፣ ቁርሴን በልቼ ከሥራ መልስ ብሩክ ጋ ለመሄድ ጥቁር ሻርፔን ቦርሳዬ ውስጥ ከትቼ ወደ ቢሮዬ ሄድኩ።

አይኔን አላመንኩትም፤ ብሩክ ወንበሩ ላይ ፋይል ከምሮ አንገቱን ደፍቶ ይሠራል። ሳየው ደነገጥኩ፤ በደመ ነፍሴ ብሩኬ ስለው ኮስተር እንዳለ በማያቀርብ አስተያየት እያየኝ "ሰላም ሊዲያ” አለኝ።

ሁላችንንም ፊት ነሳን። በሌሊት ሥራ ይገባል፣ አምሽቶ ይወጣል፣ ምሳ ብቻውን ይበላል። አይኑ አባብጦ እንባ ያሸበረው ፊት አይበታለሁ፤ ማንም እንዳያጽናናው መንገዱን ዘጋጋው። አለቃችን እንኳን በረታህ ብሎ ሲጀምር አዎ ይልና ከአጠገቡ እብስ ይላል፣ ወይ ደግሞ ወሬ ይቀይራል።

ወንድሙ ካለፈ በአስራ አራተኛው ቀን ላይ ብሩኬ ደህና ነህ? ግን ምነው እራቅከኝ? አልኩት።

"ትንሽ ቀን ነው የምፈልገው ደህና እሆናለሁ፤ ሁሉም ደህና ይሆናል" ብሎኝ ጭጭ አለ።

በቅጡ አንዳላጽናናህ እኮ መንገዱን ዘጋኸው፤ : ሰው በሚያስፈልግህ ጊዜ ነው ከሰው የራቅከው አልኩት። አየኝ፣ አጎነበሰ ቀስ ብሎ ቀና ብሎ እያየኝ ከትንሽ ዝምታ በኋላ...

“ይሄውልሽ ሊዱ ማጽናኛችን የጎደፈ ነው፤ አንዳንዱ ቤትሽ የሚመጣው ለወጉ ነው፤ አይኑ ላይ ምንም እንባ ሳይታይ ወንድሜ፣ ወንድሜ እያለ ድንኳን ውስጥ ይገባል። አጠገብሽ ይመጣና ምን አገኘው? ገጪው ተያዘን ወንድሜ፣ ሰላምተኛዬ፣ ጥሩ ሰው፣ መከታዬ ይላል። ሐኪም ቤት አልወሰዳችሁትም? ጥያቄ በጥያቄ። የሚያስቆጭ፣ ሐዘን የሚፈጥር ጥያቄ፣ የሚያጎላ ጥያቄ። እንዳልታዘበው፣ እንዳልቀየመው ሐዘንህን መጥቻለሁ ፊቶች፣ ፊታቸውን ለማሳየት የሚጋጋጡ ሰዎችን ጋቢ ለብሶ መታዘብ ሕመም ነው።

በጣም ከባድ ነው ሊዱ፤ ሁሉም የሚጽናናበት መንገድ ሊሆን ይችላል እኔ ግን አልቻልኩም፤ የአጽናኞቼን መንገድ የዘጋጋሁት ሆን ብዬ ነው። ለማጽናናት ስለጉዳዩ ማተት የግድ አይደለም እኮ፤ አብሮ መሆን በቂ ነው፤ ማቀፍ በቂ ነው። ጊዜ ኃያል ነው፤ የማያዶለዱመው ሕመም የለም።

ወንድሜ ጋሽዬ ለእኔ ብዙ ነበር። እሱ ነው ያሳደገኝ፤ የምምለው እንኳን በእሱ አይደል? ለቁም ነገር እንድደርሰ ያልሆነልኝ አልነበረም፤ ኃላፊነቱ ነበርኩ፤ የበኩር ልጄ ነው የሚለኝን ወንድሜን ነው ያጣሁት።

ጉዳዬ ከእግዜር ጋ ነው።

እሱ ነው የተመሳቀለውን እጦቴን በመልክ በመልኩ በእግዜርኛ የሚያበጃጅልኝ፤ እንጂማ በፍጡር ሊያውም ማብሸቅ በሚመስል ማጽናኛ አልድንም። ለዚህ ነው ከቀብር ጀምሮ ቤተክርስትያን የማድረው። ከአማኝ ጥቅማጥቅማችን አንደኛው ከአቅማችን በላይ የሆነ ሁነት ሲጋረጥብን እግዜርላይ ሙጥኝ ማለት አይደል? ከትናንት ዛሬ በደንብ እየበረታሁ ነው፤ የታመንኩት አምላክ እያጽናናኝ እያጸናኝም ነው።"

የብሩኬ አወራር፣ ሁኔታው፣ ሕመሙ አንጀቴን አላወሰው። አይኔ ላይ ያቀረረው እንባ አለመውረድ አልቻለም። አንድ ነገር ብቻ አልኩት

እግዜር ያበርታህ ወዳጄ።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👏1615😢3
#አርፋጅ

አንድ ሰፈር ነው ያደግነው፡፡ አንድ ዩኒቨርስቲ ተማርን። ብሩክ ፈታ ያለ ነው፣ ጨዋታ ያደምቃል፣ ጨዋታም ያውቃል። እሱ ካለ የሳቅ ድምጽ አይጠፋም። ስድስተኛ ክፍል አልፈልግህም ተብሎ የተላከለትን ደብዳቤ አባቱ አግቶበት
የመታውን ጠረባ፣ ለፍቺም ደርሰህልኛላ እያለ የሚጦልበውን ጡለባዎችን እየቀመመ ሲያጫውት አፉን ከፍቶ የማይስቅ አልነበረም።

ታላቅ ወንድሙ ላይ የሚሠራውን ተንኮል፣ የግድያ ሙከራ የሚመስሉ ድብደባዎችን ኮስተር ብሎ በፌዛም ፊቱ እያወጋ ያዝናናን ነበር። ግሬድ ሲሰቅልም፣ ሲሾቅም ማላገጡ የሚጠበቅ ነው። በዙሪያው የማንጠፋው ፍሬንዶቹ ላይ እንዳይደብረን አድርጎ ለጨዋታ ፐርፐዝ ብቻ ይቀልድብናል።

ብሩክ እንደ ጃካራንዳ ዛፍ በዙሪያው ሚያጅበው አይጠፋም፣ ሰው ይወደዋል። ከሰው ጋ እይጋጭም፣ መከባበር የማይደራደርበት ዋነኛ ፖሊሲው እንደሆነ በደንብ የሚቀርበው ሁሉ ያውቃል፣ የጠበቀ ወዳጅነት ያለን ደግሞ በይበልጥ እናውቃለን።

ብሩክ ለእኔ ወንድሜ ነው የማልለው ባልጀራነትን ማሳነስ ስለሚመስለኝ ነው። ብዙ ሳቅ እና ጭንቀቶችን ተጋርተናል። በድዬ ሳለሁ ለእኔ አግዞልኛል፣ እስከ ድክመቱ ተቀብየዋለሁ፤ ጓደኛዬ ነው፣ ምንም ሳይኖረን ጊዜ ብቻ እያለን ነው ነፍሳችን የተናበበው፤ የጓደኝነት ትርጉም መተንተን ሳንጀምር ነው የተወዳጀነው።

እኔ ታላቅ ወንድሜ የጀመረውን ቢዚነስ ተቀላቅዬ በሂደት ብዙ ሳንቲም ማግበስበስ ጀመርኩ። ብዙ ሀብት ባገኘሁ ቁጥር መፍጨርጨሬ ጠነከረ፣ ነገሮችን በውሎዬ ስለምመዝን እነጫነጫለሁ፣ ብሩክ ነገሮችን ከእሱ አንጻር ስለሚያይ መነጫነጬ አይገባውም።

ብሩክ ቀልደኝነቱ መፍዘዝ ጀመረና መገለጫው ያልሆነ ጨለምተኝነት ወረሰው። ምሬቱን ቀልቤን ሰብስቤ አሰላስዬ አላውቅም፣ መንገዱን ለመደልደል አልጣርኩም። ከእጮኛው ጋ የሚያጋጥመውን ግጭት በምሬት ሲነግረኝ ቀልቤን ሰብስቤ ከጊዜያዊ ስሜት የገዘፈ ይሆናል ብዬ አላሰብኩም።

የድሃ ልጅ መሆኑ፣ አይዞህ የሚለው አለመኖሩን ሲጠቅስ አብሬው ከማሸብሸብ የዘለለ ጊዜ ሰጥቸው ምን ላግዘው? ከእኔ ምን ይጠበቃል? ብዬ ለአፍታ አሰላስዬ አላውቅም።

እድገት ላይ በመመሰጤ ያሉኝን በረከቶች ለማስተዋል አልተቻለኝም ነበር። ያሉንን እየጣልን የምናመጣው አዲስ ስኬት እንደምን የምንፈልገውን ደስታ ሊያመጣልን ይቻለው ይሆን??

ለሥራ ኔትወርክ የማይሰራበት ቦታ ከርሜ ስመጣ እንድንጠጣ፣ እንድንስቅ ደወልኩለት ግን ስልኩ ዝግ ነው። ደጋግሜ ደወልኩ፤ አሁንም ስልኩ ዝግ ነው። ስልክ ማጥፋት፣ ስልክ አለማንሳት፣ ለብቻው መሆን አዲስ ያመጣው ፋሽኑ መሆን ጀምሯል። ቤቱ ልሄድ ተነሳሁ።

ፀሐዩ ሀሩር ነው፤ ዘንድሮ ፀሐዩን ለማምለጥ እንደዝናብ መጠለል እና መሮጥ መጀመራችን አይቀርም። የድሮ ሰፈሬ ደረስኩ፣ የነ ብሩኬ ደጅ ላይ ድንኳን ተደኩኗል፤ ብሩኬ አያቱ ጠንካራ ሕመም እያንገላታቸው እንደሆነ ነገሮኝ ነበር።

አያቱ በሕይወቱ ደማቅ ስፍራ አላቸው፤ ይወዳቸዋል፡፡ እንደ ወንድሙ ነበር የሚያዋራቸው፣ እንደ ጓደኛቸው ነበር የሚያጫውቱት። ከልጅነት ጀምሮ የምናቀውን ሰው ማጣት ሕመሙ ብርቱ ነው። ድብርት እና ምሬት ሳይጣባው አያቱ ሳይተኙ ለመድረስ ነበር የሚሮጠው።

እርምጃዬን ቀስ እያደረኩ ወደ ድንኳኑ ስሄድ የሰፈራችን ለቀስተኞች አይን እኔ ላይ አረፈ፣ አጎነበስኩ። ቀስ ብዬ የድንኳኑ መግቢያ በር ላይ ያገኘሁት ወንበር ላይ ቁጭ አልኩ፣ በቀስታ ቀና ብዬ ብሩኬን በአይኔ ሳስሰው ወንበርተደርድሮ በተቀመጠ ፍራሽ ላይ የደከሙ አያቱን አየኋቸው፤ ፍጥጥ ብዬ እንዳየኋቸው አስታውሳለሁ።

ከአጠገባቸው እናቱን አየኋት፣ በጥሩ መንፈስ አላየችኝም፤ አይኔ ወደ ተሰቀለው ፎቶ ተምዘገዘገ። ከዛ ሰዓት በኋላ የሆነውን ብዙ አላስታውስም። ለቀበሌ መታወቂያ ብሎ አብረን ሄደን የተነሳነው የብሩኬ ፎቶ ተሰቅሏል። በጣም እንደጮህኩ አስታውሳለሁ፤ እናቱን ሂሩቴን እየወደቅኩ፣ እየተነሳሁ የሆነውን ለመጠየቅ ፍራሹ ጋ ለመሄድ መሞከሬንም አልረሳሁትም። የሆነውን ሁሉ ፡ አለማወቄ ተገለጸላቸው፡፡ ረጭ ያለው ለቅሶ ቤት ታወከ፤ ሁኔታዬ ያሳዘናቸው ሰዎች አብረውኝ ያለቀሱ ይመስለኛል።

አያቱን አንቄ ጋሽ በላይ ጓደኛዎት የት ሄደ፣ ብሩኬ የት ሄደ? አልኳቸው። በዛለ እጃቸው አቅፈውኝ በትኩስ እንባ ታጅበው እጁን በእጁ በላ አሉኝ። እግሬ አልጸና ያለ ይመስለኛል፤ ብዙ ሰዎች ያዙኝ፤ ክንዴን ክንዴን ብዬ ጮህኩኝ፤ ሰው ለካ እንዲህ ደካማ ነው፤ የቻልኩት መጮህ እና የሆነውን መካድ ነበር።

በቀን ብዛት ተበረታታሁ ያወራነውን ሳሰላስለው ኋላ መቅረት ሲንጠው እንደነበር ገባኝ። ጨለምተኝነቱ ለመኖር ያለውን ፍላጎት ቀድሞ እንደገደለበት ገባኝ። ለካስ ማስተዋል አቅቶኝ ነው እንጂ ሁሉም ነገሩ ይገባ ነበር። አብረን ብንሆንም ለካ ተለያይተን ነበር፤ ለካ እሱ ነበር ጓደኛዬ እንጂ እኔ ጓደኛው አልነበርኩም። አናቱ ላይ በፍጥነት የወረረውን ሽበት ከ"stress"፤ ከመብሰልሰል የተፈጠረ መሆኑን አልጠረጠርኩም ነበር።

ተሳክቶለታል የምባለው እኔ ነገሮች ሲጠሙብኝ፣ አንዳንድ ነገሮች ሲከፉብኝ ይቺ ዓለም እንደምትሰለቸኝ አውርቼው አላውቅም።

ራሴን ልገድለው እንደነበር ነግሬው አላውቅም። ሽራፊ ፈገግታ በሀሩር ፀሐይ ጤዛ እንደመፈለግ ሆኖብኝ ሳለ፣ የሞከርኩት ሙከራዎች ሲከሽፉ፣ ከሰው ሁሉ አነስኩኝ ስሜቴ ሲበላኝ፣ ብቻ መሆን ሲጨፍርብኝ፣ አለመፈለግ ስሜት ሲወዘውዘኝ፣ ያለኝን ነገር ሁሉ ያፈሰስኩበት ተስፋዬ ሲጠፋ፣ ሕልሜ ሰፍቶኝ ስንከላወስ፣ የምሸሸግበት ጥግ ሳጣ፣ በማምነው ሰው ስካድ፣ ዕድለቢስነት እንዳልጠራጠር አድርጎ ሲመሰክርብኝ ራሴን ልገለው ዳድቶኝ ነበር። መዳዳቴን እንዴት ድል እነደነሳሁት ሳልነግረው!

አምላኬ ጋር ሙጥኝ እያልኩ፤

አንዳንዴ በረከቶቼን ፈልፍዬ ለራሴ እየተረኩ፣

አንዳንደ ጭላንጭል ብርሃኔ ላይ ተመስጬ፣

ብሞት የምሰብራቸውን ሰዎች አዝኜላቸው።

አንዳንዴ ክችች ያልኩበትን ጉዳይ እያላላሁ፣ አንዳንዴ ግትርነቱን እየገሰጽኩ፣ አንዳንዴ ሆስፒታል ያሉ አካላቸው የማይታዘዝላቸው ነፍሶችን እየረዳሁ፣ አንዳንዴ እስረኞችን እየጠየቅኩ ነው ራሴ ላይ የራራሁት ሳልለው
ይሄ ትግሌ ለብሩኬ ትርጉም ሊሰጠው እንደሚችል ማሰብ አልተቻለኝም ነበር። የምንወዳቸውን ሰዎች ምን ያህል እንደምንወዳቸው ካለ እጦት እንዴት መረዳት ያቅተናል? ለራስ ሰው አለመድረስን ያህል አርፋጅነት የለም።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
32👍11😢9
#እግዜር_አደራውን_ሲበላ

ግርግር ከማይወዱ ጓደኞቼ ዛብሎን አንደኛው "ነው። እይታዎቹ በወፍ በረር የተኮረጁ አይደሉም፤ ስለማያውቀው ነገር ከተወራ ይሰማል ረጋ ብሎ ስለሚያወራ፣ ስለሚያውቀው ነገር ብቻ ስለሚያወራ እያዳመጠ ስለሚያወራ፣ መናገር .. ሲጀምር የማይሰማው የለም።

ጨዋታው ብዙ ሰው ላይ ያለው እመነኝ፣ ቅዱስ ነኝ ዓይነት ስብከት የለበትም።

ክላስ አለው!!

አጠገቡ ያለ ሰው ስለማያውቀው ነገር ሲቀባጥር፣ ዛብሎን ደግሞ ስለጉዳዩ በደንብ እውቀት ካለው ለስለስ አድርጎ ቀባጣሪው የቀባጣሪነት ስሜትን ሳያሳድርበት ደርበብ ባለ መልኩ ሐሳቡ ላይ ብቻ አተኩሮ ሙግት ውስጥ ሳይገባ ስለሚያውቀው ነገር ይናገራል። እንደዚህ ዓይነት ግለሰብ ሰውዬው የበታችነት ሳይሰማው፣ አላዋቂነት ሳይታገለው የያዘውን መረጃ አልያም አቋም እንዲመረምር ያስችላል።

ዛብሎን ጺሜ አደገ፣ ጸጉሬ ተንጨባረረ ብሎ ጸጉር ቤት እንደማይሄድ የጸጉሩ መንጨባረር እና የጺሙ መንዥርገግ ምስክር ናቸው። ዘናጭ አይደለም ግን ንፁሕ ነው። ከሁሉ የሚገርመኝ ካላሳቀው አይስቅም። በጋራ ተሰብስበን ሁላችንም እየሳቅን በእርጋታ ሳቃችን እስክንጨርስ ጠብቆ በትንሽ ፈገገግታ አልገባኝም ብሎ ስለሳቅንበት ነገር ማብራሪያ ይጠይቃል፤ ተጨብጭቦለታል ብለን ለምናጨበጭብ ሰዎች አጀብ ነው ይሄ፡፡

ካፌ ውስጥ እንደተቀመጥን ዛብሎን አስተናጋጇን በምልክት ጠራትና መጥታ

'ምን ልታዘዝ'

"ተቆራጭ አምጭልኝ" አስናጋጇ ስትሄድ ጠብቄ

የገና ጾም አትጾምም እንዴ?

“አልጾምም!“

ለምን?

“እናቴ ስትሞት ነው ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር ያለኝ ቁርኝት የተፋታሁ፤ ተስፋ ቆረጥኩ፣ የምለፋበት ምክንያት አጣሁኝ። ድሮ ቤተክርስትያን ስሄድ ነጭ ሐበሻ ቀሚስ የለበሱ፣ ሹርባ የተሠሩ እናቶች ሳይ፣ ሥራ ስይዝ ለእናቴ እንዲህ እገዛለሁ እለው ነበር እግዚአብሔርን። ቆርበው ከቤተክርስትያን በር ላይ መኪና የሚጠብቃቸው እናቶችን ሳይ እኔ ለእናቴ እንዲህ እንደምንሆን ለእግዚአብሔር ፈገግ እያልኩ አጫውተው ነበር። ስማር እንቅልፌ እየመጣ እግሬን ውሃ ውስጥ ዘፍዝፌ የማጠናው ከእግዜር ጋር የተጨዋወትነውን ምኞቴን ለማሳካት ነበር። እሱ እኮ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ነው የሚለው እያልኩ።

ሱሰኛ ያልነበርኩት እናቴ ልጄ እኮ እንደዚህ ዓይነት ነገር አይወድም፤ የእኔ ልጅ እኮ ብላ እንድትጎርር ነበር። ሕልሜን ከእናቴ ጋ ብቻ ማቆራኘት አልነበረብኝም። ግን እኮ ወድጄ አይደለም፤ ቤተሰቦቿ አረገዝሽ ብለው ሲያባርሯት፣ አባትየው ሲክዳት፣ ምድረ በዳ ላይ ተነጥሎ እንደቀረ ሰው እኔን አገሯ፣ ዓለሟ አድርጋ የተዋደቀችልኝ ናት"

ፊቱ ቅዝቅዝ አለ... ትኩስ እንባ አይኑ ላይ ቅርርር ሲል አየሁ። ከዚህ በፊት አስተውየዋለሁ፤ ስለ አምላክ ሲወራ አስተያየት አይጎጥም። በቤተክርስቲያን ስናልፍ በእጃችን እያማተብን ከጉልበታችን ሸብረክ ስንል እሱ ግን ልክ መንገድ ላይ የምናውቀውን ሰው አግኝተን ሰላም ስንል ስለማያውቀው ብቻ እልፍ ብሎ እንደሚሄደው ልክ እንደሱ አልፎ ይሄዳል።

ውለታ የዋለለትን ሰው የእግዜር ስምን እያጠቀሰ ሲመርቀው አሜን አይልም። ተመጽዋች ምጽዋት ሲጠይቀን ከሌለን እኛ እግዜር ይስጥልን እንላለን ወደ እሱ ዞሮ ሲለምነው የለኝም ይላል።

እግዚአብሄሩን አኩርፎት እንደሆነ ካስተዋልኩ ቆየሁ። በዙሪያው የሚያፈቅረው የለም፤ አለማፍቀሩ ከፍቅር ሾልከው የሚመጡ ስጋት፣ ተስፋ እና ስስት የሚባሉትን ከውስጡ አሽሽቶለታል። አንድ ቀንም ለእግዜር ስሞታም፣ ውዳሴም ሲያቀርብ አይቼው አላውቅም። ዝም ብዬ ሳየው በለሆሳስ ብቻውን ከእግዚአብሄሩ ጋር የሚዋቀስ ነው የሚመስለኝ።

ሳየው በዝምታ እግዜሩን ለምን አደራኽን በላህ የሚለው ነው የሚመስለኝ!!!

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
20🤔7
#ኀሰሳችን_ከሽፎ_እንጂ

ጥዑም ጊዜ ላይ ነበርን። ወይን እየተጎነጨን፣ እየተሳሳምን፣ ድንገት ሳላቅድ፣ ሳልቀምር፣ ሳላስብበት ከአንደበቴ የውስጤ እውነት አመለጠኝ፡፡

ትክ ብዬ ሳያት ፈገግ ብላ “እችን የመሰለች ልጅ ጠበስክኣ?" አለችኝ ወደ ራሷ እያመለከተች፤ በትንሹ ፈገግ አልኩ። ፈገግታዬን እንደ መስማማት ቆጥራ በሚያምር ፈገግታዋ እያየችኝ "እናትህማ መርቀውሃል" ስትለኝ ይሄኔ ነበር የልቤ እውነት ያመለጠኝ።

ታውቂያለሽ ግን አንቺ ሕልሜ እንዳልሆንሽ፤ የመጣሽበት መንገድ፣ ዕቅድሽ፣ መርሕሽ ከእኔ ጋ መች ይሄዳል? አልኳት።

ሽማግሌ ከላክሁኝ በኋላ፣ በጋራ ስለምንወልዳቸው ልጆቻች ስናወራ ከርመን እንዴት እንዲህ ይባላል? ሁሉ እውነት እንዴት ይወራል? የልብ እውነት ሁሉ ይዘረዘራል?! ትበሳጫለች ብዬ ነበር ግን ደግሞ የጠበኩትን የፊት መለዋወጥ አላየሁም። ረጋ እንዳለች፣ ፊቷ ሳይለዋወጥ ትክ ብላ አየችኝ፤ ቅፍፍፍ የሚል  ስሜት ዋጠኝ፤ ምን አለ አስማተኛ በሆንኩ እና እንዳልሰማች ማድረግ አልያም እንዳልተናገርኩ መሆን ብችል።

ቃላቱን እርግጥ አድርጋ

“ትክክል!! ጊዜው አሳዝኖን ነው አብረን የሆነው፤ አብረን ሆነን በስሱ ሌላ የፍለጋ ሙከራ ስላልተሳካልን ነው የምንጋባው። አንዲት ቀን 'Messenger ህን ከፍቼ አይቻለሁ፡፡ የምታወራቸውን እንስቶች ቀልብ ለመግዛት የምትሄድባቸውን መንገዶች፣ መሻፈዶች፣ ላጤ ነኝ ጨዋታዎች፣ ብልግናዎች ተመልክቻለሁ፤ ሁሉም ከእኔ ጋ አንድ ዓይነት ነበሩ። የማደርገውን ነበር የምታደርገው፤ ከፍቶኝ ነበር እንዳላኮርፍ፣ እንዳልጨቀጭቅህ፣ እንዳልጣላህ ካንተ አለመሻሌ አሸማቀቀኝ። የብዙ ሰዎች ትዳር እንዲህ እንደሆነ አይቻለሁ፤ ከገቡ በኋላ በልጆቻቸው ይጽናናሉ፤ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሚስትና እና ባላቸውን እየከሰሱ ኑሮን ይገፉታል።

ለዛ ነው እንከን የለሽ ትዳር የሚያስሱት ቆመው የሚቀሩት! በቆዩ ቁጥር መለኪያቸውን እየቀየሩ ካጣጣሉት፣ ከተጠየፉት የኑሮ ቀንበር ላይ ራሳቸውን ያገኙታል። ለዛ ነው እንደሚታረድ በግ ሁሉን እያወቅኩ ሽማግሌ ስትልክ፣ ቀለበት ስታጠልቅልኝ፣ የልቤን እውነት አፍኜ የምከተልህ።"

ሲዘበራረቅብኝ ይታወቅኛል። ግራ ገባኝ፤ የሕይወት አጋርን በዚህ ደረጃ አለማወቅ ምን ይባላል? እችን ልጅ ነገሮች በዚህ ደረጃ ይገባታል ብዬ አላሰብኩም። ሴት ልጅ ትታልልህልሀለች እንጂ አታታልላትም እኔ እንዲህ እንደሚሰማኝ እንጂ እሷ እንደዚህ እንደሚሰማት አላውቅም ነበር።

ለምን ታድያ አብረን እንሆናለን ሁለታችንም እንዲህ
ከተሰማን?

"እንሂድ"

ምን አልባት ጊዜያችን፤

ምን አልባት ዕድሜያችን አሳዝኖን?

ምን አልባትም በዙሪያችን ያለ ውትወታ?

ምን አልባት ዘራችንን ለመተካት ካለን ፍላጎት?

ምን አልባት መላመዳችን እንዳንለያይ አግቶን ይሆን?

ምን አልባት አንዳችን ለአንዳችን ካለን ውስጣዊ ስሜት ይሆን?

ምን አልባት በዙሪያችን ካሉት ሰዎች የበለጠ ስለምንዋደድ??

ምን አልባት በስሱ ሌላ ለማግኘት ያሰስነው ኀሰሳ ስላልተሳካ??

ሰው የልቡን ሁሉ አለማውጣቱ ይሆን ቁርኝታችንን
ያላሳደፈው? ባለጋራችንን አለማወቅ ጠቀሜታ ይኖረው ይሆን? አንዳንድ ዕውቀት ምቾት አይሰጥም። ዕውቀት ትካዜን ታበዛለች እንዲል መጽሐፉ፤ አንዳንድ ውይይቶች ሽንቁር ያበጃሉ። የጀመርኩትን ወይኔን በአንድ ትንፋሽ ወደ ጉሮሮዬ አንቆረቆርኩት።

እንደዚህ ዓይነት ሎጂክ ተዘባዝቦ ግንኙነት፣ ትዳር መመሥረት ይቻል ይሆን? እንዳለችው ፍርሀት ነው? እጦት ነው? መላመድ ነው? ምንድን ይሆን በትክክል ያጋመደን?

ምን አስቸኮለን? ምን አሸበረን? ይሄን እውነታ ከተዘራዘሩ በኋላ እንዴት ጎጆ ይቀለሳል? ልጅ ሳይመጣ፣ ንብረት ሳናፈራ፣ ኑሮ ሳይንጠን የግንኙነታችንን መዓዘን መገምገም እንዳለብን ነው የገባኝ። አሁን የምጎዳት ነገ ከምሰብራት አይበልጥም፤ ዛሬ የሚሰማኝ ሕመም ነገ ከሚጋረጥብኝ መከራ አይበልጥም።

ማሬዋ ሰው ውድ ፍጡር ነው። ችኮላችን ብልጣብልጥነታችን፣ በራሳችን ማስተዋል መንጠልጠላችን የእኛ የራሳችን የሆኑት ሰዎች ጋ አንድንሸዋወድ ያደርገናል። ጊዜ እንውሰድ፣ ተነጣጥለን ዙሪያችንን፣ መንገዳችንን እንመርምር፤ ብልግናችንን ይቅር እንበለው። የቆምንባቸውን ስፍራዎች እንቃኛቸው፣ ከፈጸምናቸው ጥፋቶች ጋ እንፋጠጥ፣ እናርማቸው፣ እናበጃጃቸው። ብቸኝነት አባብቶን፣ አቻ ግፊት ወትውቶን፣ መላመድ አሳስሮን፣ የቤተሰብ ግፊት ገፈታትሮን ኑሮ አይመሰረትም። የሁሉም ጓዳ እንዲህ ነው ተብሎ አዲስ ጎጆ አይበጅም፤ ሁሉም ሄዷል ተብሎ እንኳን በስሕተት መንገድ በትክክለኛ መንገድ መሄድ ተገቢ አይደለም።

ከመጣንበት መንገድ የምንሄድበት ሩቅ ነው። ራሳችንን ከእርስ በእርሳችን ነጣጥለን እናጢነው። የአሰተውሎት መንገድ ደግሞ አሜን ካልነው ባሻገር ያለውን እውነታ መጋፈጥን ይጨምራል።

ያኔ የውስጣችን እውነት ፍንትው ብሎ ይታየናል፤ ለውሳኔም ይረዳናል። ስሕተታችንን ለማረም ከፍርሀት ጋ መጋፈጥ የመጀመሪያው እርምጃ ነው።

ከዚህ ሁሉ መንገድ በኋላ መመለስ እንዳስፈራት ታስታውቃለች። እኔም የወጠንኩትን፣ የለመድኩትን፣ የወሰንኩትን ዳግም ለመመርመር እና ለመከለስ ሳስብ ደስስ የማይል የሚቀረዝዝ ስሜት ሲወረኝ እየተሰማኝ ነው።

🔘አድኀኖም ምትኩ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
22👍2