አትሮኖስ
277K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
448 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#አላገባህም


#ክፍል_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ



///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ  አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን  መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡

‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት

‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››

‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡

አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን  አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ

‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ  ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡

‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››

‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››

‹‹ድንግልናሽን?››

‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››

‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…

‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡

‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››

‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››

‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››

‹‹ማለት?››

‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡

‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››

‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››

‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡

‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡

‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››

‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ  ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››

‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››

‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››

‹‹ምን ያስፈራሀል?››

‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ  መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››

‹‹እንዴት …?››

‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››

‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››

‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››

‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››

‹‹ማለት?፡፡››

‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡

‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡

‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡

‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡

‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››

‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››

‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡

‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡

አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹ማለት?››

‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል   ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››

ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ  ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት  ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን  ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡

በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡  ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ  ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች   እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡

በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት  ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
#አላገባህም


#ክፍል_ስምንት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡

‹‹እሺ ንገረኝ…ምንድነው ያሳቀህ?››

‹‹በጣም ነው እንጂ የሚያስቀው…ማንም ሴት እንዲህ አይነት መደራደሪያ አቅርባልኝ አታውቅም››

‹‹እኔ እኔ ነኝ ..ስለሌሎች ሴቶች አላውቅም፡፡››

‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ አለሽ እንዴ?››በአእምሮ ሲያብሰለስል የነበረው ጥያቄ ጠየቃት፡፡

አፈጠጠችበት..ደነገጠም ..ግራ ተጋባም

‹‹እንዴ …ምን መጥፎ ነገር ተናገርኩ?››

‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ ቢኖረኝ እዚህ ከአንተ ጋር ምን ያንዘላዝለኛል?፡፡››

ወደራሱ ጎተተና ከንፈሯ ላይ ተጠጣበቀባት…ተቃውሞ አላሰማችም..እንደውም ቀስ ብላ እጆቾን አነሳችና በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመች…አልጋውን ለቃ እየተንሳፈፈች እንደሆነ አይነት ምትሀታዊ አይነት ስሜት እየተሳማት ነው፡፡

የልቧን ምት ፍጥነት መቆጣጠር ስላልቻለችና መተንፈስም ስለከበዳት እየፈለገች ግን ከንፈሯን ከከንፈሩ አላቀቀችና

፣‹‹የሚጠጣ ነገር ይኖራል?››
ስትል ጠየቀችው፡፡መጠጥ የጠየቀችው በወሲብ ወቅት ድፍረት ይሰጣል ሲባል ስለሰማች ነው፡፡

‹‹አዎ አለ፡፡››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ… ለእሱም ለእሷም መጠጥ ይዞ መጣና ጠረጴዛውን ወደ አልጋው አስጠግቶ ከጎኗ ተመልሶ ቁጭ አለ፡፡

‹‹ምነው ይሄን ያህል አስፈራለሁ እንዴ?››

‹‹አይ በፍፅም…..ግን ››ንግግሯን አቋረጠችና ስልኳን ካስቀመጠችበት ኮመዲኖ ተንጠራርታ አነሳችና..ከፍታ  ሰጠችው፡፡

‹‹ምንድነው?››

ተቀበላትና ተመለከተ..ውብ ቆንጅዬ የምታምር ልጅ ፎቶ ይታያል፡፡ግራ ገባውና ቀና ብሎ በትኩረት አያት‹‹ልጄ ነች…ስድስት አመቷ ነው፡፡››

‹‹ምን …?››ከተቀመጠበት ተነሳ…አፍጥጦ ፎቶውን መመለክት ጀመረ፡፡

በሁኔታው ተበሳጨች….‹‹… ዝም ብዬ እንድታውቀው ስለፈለኩ ነው እንጂ ይሄን ያህል ምን ያስደነግጥሀል…?አታገባኝ ወይ አትወሽመኝ ..አንድ ልጅ ኖረኝ አምስት ምን አጨናነቀህ…?››

በቆመበት አፍጥጦ በዝምታ ያያት ጀመር፡፡ያ ደግሞ የበለጠ ንዴቷን እንዲጨምር አደረገ…‹‹እንደውም ሁሉ  ነገር እዚህ ላይ ያብቃ ወደቤቴ ልሂድ››ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ተንደርድሮ መጥቶ ትከሻዋን ይዞ አስቀመጣትና ግንባሯን ሳማት፡፡

‹‹በጣም ነጭናጫ ሴት መሆንሽን ታውቂያለሽ?››

‹‹እንኳን››

‹‹እኔ ይህቺን የመሰለች ልጅ ስላለሽ ቀናሁብሽ እንጂ አልተበሳጨሁበሽም…በጣም እኮ ነው የምታምረው…..ደግሞ በስንት አመትሽ ብትወልጂያት ነው እንዲህ ያደገችው?››

‹‹በ17››

‹‹እና የት ነው ያለችው ..ከአንቺ ጋር ወይስ አባቷ ጋር?››

‹‹አባቷ መፀናሷን እንዳወቀ ነው ሸሽቶ ውትድርና ተቀጥሮ የጠፋው..እስከአሁን ይኑር ይሙት አላውቅም…እሷ ከእኔ ጋር ነው ያለችው፡፡››

‹‹እና አሁን እቤት ነው ያለቻ ?ብንሄድ እናገኛታለን?››

በመገረም አፍጥጣ ተመለከተችው‹‹የእውነት አሁን እንሂድ ብልህ ትሄዳለህ?››

‹‹አዎ..››ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ …‹‹ሰዓቱ ገና ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ከ10 ነው …ተነሽ እንደውም….የሆነ ነገር ገዝተንላት እንሂድ እና እናስደስታት፡፡››

እሱ ጃኬቱን ሲለብስ እሷ ከተቀመጠችበት ሳትንቀሳቀስ በገረሜታ አፏን ከፈተችና በፍዘት ታየው ነበር፡፡

‹‹አልሰማሺኝም እንዴ? ተነሽ እንሂድ››

‹‹ልጅ ማትወድ መስሎኝ ነበር››

በተራው ደነገጠ…‹‹እንዴ ምን ማለት ነው…?እንዴት እንደዛ ልታስቢ ቻልሽ?››

‹‹ቅድም የወንድምህን ልጅ ወደአንተ ይዤ መጥቼ ሳስተዋውቅህ..ከእቅፌ ወስደህ አቅፈህ የምትስመው መስሎኝ ነበር…ግን እንደዛ አላደረክም..ጉንጩን አንኳን አልሳምክም››

ወደእሷ መጣና ከጎኗ ተቀመጠ‹‹ያን ያህል ስትታዘቢኝ ነበር ማለት ነው…?ላቅፈውና ልስመው በጣም ነበር የፈለኩት….አጎትህ ነኝ ብዬ እሽኮኮ በማድረግ ከሆቴሉ ይዤው ወጥቼ ላዝናናው ሁሉ ፈልጌ ነበር..ግን አልቻልኩም…ምክንያቱም የወንድሜ ልጅ ነው ፤ስለወንድሜ ሳስብ ደግሞ በደረቷ ቢላዋ ተሰክቶባት ወለል ላይ የተዘረጋች እናቴና በገመድ የተንጠለጠለች እህቴ ነች ወደአእምሮዬ የምትመጣው…በዛን ወቅት አሰብ የነበረው ስለእነሱ ነበር …እንባዬ እንዳያመልጠኝና በሰርግ እድምተኞች ፊት እንዳልዋረድ እየጣርኩ ነበር››እንባው ከአይኖቹ እየተዘረገፈ መውረድ ጀመረ፡፡ ደነገጠችና ከተቀመጠችበት ተነሳች በእጇቾ እንባውን እበሰችና ግንበሩን ጉንጮቹን እያገላበጠች እየሰማች‹‹ይቅርታ…በጣም ይቅርታ…እኔ እንዲህ አይነት ቀሽም ሴት ነኝ…ሶሪ ወንዶችን ሰላማላምን ሁሉን ነገር ነው የምጠራጠረው…ከልጄ አባት ውጭ ሌላ ወንድ አላውቅም…ከአንተ ጋር በእንደዚህ አይነት መጠን መቀራረብና በአንድ ክፍል ውስጥ መሆን በጣም ቢያስደስተኝም በዛው መጠን አስፈርቶኛል….ለዛ ነው ያልሆነ ነገር የምቀባጥረው፡፡››

‹‹ችግር የለውም… ተረድቼሻለው››

‹‹በቃ በፈጣሪ ያልኩህን  ሁሉ እርሳው…››ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት..በጠንካራ እጆቹን በቀጭን ወገቧ ዙሪያ ጠመጠመና ከሰውነት ጋር ለጥፎ ትንፋሽ እስኪያጥራት መጠጣት…..ከዛ ለቀቃትና..‹‹በይ አታረሳሺኝ ተነሽ እንሂድ››

‹‹በእውነት ቢሆንና ብታይህ በጣም ነበር የምትደሰተው…ሙዚቀዎችህን በጣም ነው የምትወዳቸው…ግን አሁን የለችም››

‹‹የለችም ማለት?››

‹‹አሁን ክረምት አይደል..ትምህርት ስለተዘጋ አያቶቾ ወስደዋታል….የሚቀጥለውን አንድ ወር እነሱ ጋር ነው የምታሳለፈው….››

‹‹እ ያሳዝናል…እንግዲህ ምን ማድረግ ይቻላል ስትመለስ ታስተዋውቂኛለሽ››

‹ስትመለስ?››አለችና ሳቀች፡፡

‹‹ምን ያስቅሻል?››

‹‹የዛሬ ወር እኮ ነው ያልኩህ…››

‹‹ምነው የዛሬ ወር የለሁም እንዴ..?አለሁ እኮ ፤ማለቴ በፍቅርሽ አሟሙተሸ ካላጠፋሺኝ አለው..››

‹‹ይሁን እስኪ…..ለማንኛውም አስገርመሀኛል››አለችና የመጠጡን ብርጭቆ አነስታ ተጎነጨች፡፡

‹‹እድሉን እስከሰጠሺን ድረስ ገና ብዙ አሰግርምሻለው፡፡››

ከዛ ቀልል ያለ ወሬ እያወሩ ከመጠጡ መጎንጨታቸውን ቀጠሉ….

‹‹ይሞቃል አይደል?››አለችው የእውነትም በጣም እየሞቃት ነው…ያላወቀችው የሙቀቱ ምንጭ ከምትጠጣው መጠጥ ይመንጭ ወይም ከጎኗ ካለው ሸበላ ወይም ከአየር ፀባዩ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡

‹‹እኔም ሞቋኛል …››አለና ጃኬቱን አወለቀ፡፡

‹‹እኔስ ቀሚሴን ላውልቅ?››አለችውና ሳቀች፡፡

‹‹ይቻላል..ቆይ እንደውም..›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ወደሻንጣው በመሄድ ከፈተው፡፡ምን ሊያደርግ ነው ብላ በትኩረት እየተከታተለችው ነው፡፡

ስስ ቁምጣ እና ቲሸርት አወጣና…እንቺ  ቀሚሱን አውልቂና ይሄን ልበሺ አለና ለራሱ ሌላ ቢጃማ በማውጠት  ሱሪውን ለማውለቅ ቀበቷውን መፍታት ጀመረ፡፡

‹‹ምን እያደረክ ነው?››

‹‹ሱሬዬን ልቀይር ነዋ….››

ሱሪውን ወደታች አወለቀ..ከዛ ከላይ የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ..በነጭ ፓካውትና በሰማያዊ ፓንት ብቻ በሁለት ሜትር ርቀት ቆሞ ስትመለከት ሰውነቷን ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ነገር አንዘረዘራት፡፡በልብስ ከሚታየው ይልቅ እርቃኑን ያምራል…ደግሞ ከፊል ሰውነቱ በተለያዩ ማራኪ ንቅሳቶች የተዥጎረጎረ ነው፡፡

‹‹ምነው ፈዘዝሽ?››ብሎ አሳፈራት፡፡

‹‹ምን ፈዛለው…እንደ ሸራ በስእል ተዥጎርጉረህ የለ እንዴ?››

የሚቀይረውን ቢጃማ ሱሪ አነሳና በእጁ እንደያዘ‹‹ያምራል አይደል…?እስኪ በደንብ ተመልከቺው ››አለና ይበልጥ ወደእሷ ተጠጋና ስሯ ቆመ፡፡

ዝም አለች ..ጎትቶ አስነሳት‹‹እንዴ ምን እያደረክ ነው?››
#አላገባህም


#ክፍል_ዘጠኝ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///

‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡

ይህ ምሽት ከዘሚካኤል ጋር በፍቅር ከመውደቅ  ጋር ወይም ከእሱ ጋር የወደፊት  ከህልም ከማለም ጋር  ምንም ግንኙነት አልነበረውም። እና ሁሉም ነገር የሚከናወነው ለአካላዊ ደስታ ብቻ ተብሎ ነው። የልጅነት ፍቅረኛዋ ለዚህ  ሁሉ አመታት  የሆነ ነገሯን  ሰርቆባታል እና አሁን ሊመልስላት ይገባል ። እና ጉዳዩ ያ ብቻ ነበር።

ጠረጴዛ ላይ ያለው ብርጭቆ አነሳና ከተጎነጨለት በኋላ  እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነባት ፡፡
፤ዝም አለች…እጁን በአንገቷ ዙሪያ አሻግሮ በቲሸርቱ ስር አሾለከና ወደጡቷ  መጓዝ ጀመረ..ሽምቅቅ አለች፡፡

‹‹ዘና በይ እንጂ። ይህ ለሁለታችንም ጥሩ ይሆናል፣ ቃል እገባልሻለው።›› መልሶ እጁን አወጣና ወደአልጋው ላይ ቀድሟት በመውጣት እጇን ይዞ ወደ አልጋው እየሳበ ።

‹‹ተነሽ በቃ  እንተኛ። ››አላት፡፡

ዝም ብላ ተጎተተችለትና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋው ላይ ወጣች ።መናገር አልቻለችም፣ የልቧ ፈጣን ምቶች በጉሮሮዋ ላይ ተስፈንጥረው ሚወጡ ይመስላሉ።ወደራሱ ሳበና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡እና እጆቹን ፀጉሯ ውስጥ አስገባና ይልግላት ጀመር…ከመደንዘዞ የተነሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡ከዛ አንገቷን ..ጆሮዋን መሳም ጀመረ …ቃተተች.፡፡ወደታች ዝቅ አለና ቲሸርቷን ገለጠና ከእንብርቷ ጀምሮ እየላሰ ወደላይ ወጣ…ጡቶቾ ጋር ደረሰ የቀኝ ጡቷን ጫፍ በምላሱ እየላሰ የግራውን ጡቷን በእጆቹ እየጨመቀ ያፍተለትላት ጀመር…በፈጣሪ… እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን በፍፁም አታውቅም….ጡት ለተሳማ እንዴት ነው መላ ሰውነት እንዲህ ቀልጦ የሚንሳፈፈው…?.በጣም ያስገረማት ጉዳይ ነው፡፡

‹‹ እሺ በቃ አሁን….››ተንተባተበችና እንደምንም ጨክና  ከጡቷ አላቀቀችው

‹‹እስከ ሞት ድረስ የፈራሽ ትመስያለሽ። ምንድነው ችግሩ?፧››ሲላት እንደምንም እያጎለበተችው የነበረው ትንሹ ድፍረት ጥሏት ሄደ…ይሄንን ደግሞ እሱም በግልፅ ማየት ይችላል…፡፡

‹‹መብራቶቹን ማጥፋት እንችላለን?››ብላ በሹክሹክታ ጠየቀችው።

‹‹አላደርገውም።…ውብ እርቃኗን ለማያት ለቀናት ስለእሷ ሳሰላስል የሰነበትኩላትን ልጅ  ሳገኛት …በጭለማ….አይ አይሆንም ..አንቺን ለማግኘት ያን ሁሉ ጥረት የጣርኩት በጨለማ ውስጥ ፍቅር ለመስራት አይደለም።››ተቃወማት፡፡

ጡቶቿ ትንሽ ነበሩ፣ ዳሌዋ ጠባብ እና የልጅ ነበር። ጉንጯን ነካ፣ በዓይኑ ያልጠበቀችው ልስላሴ  እና ፈገግታ ተመለከተች። ' ለመቃወም አፏን ከፈተች እሱ ግን ጣቱን  ከንፈሯ ላይ አሳረፈ።‘

‹‹አትልፊ አልስማማም››አለና የዋናውን መብራት ማብሪያ / ማጥፊያ ለማጥፋት አልጋውን ለቅቆ ወረደ , ደማቁን ብርሀን ቢወገድም አረንጓዴና ደብዛዛ ብርሀን ግን  አሁንም  ቤቱን እንደሞላው ነው፡፡  ከላይ የለበሰውን ካኔቴራ አወለቀና እርቃኑን ወደአላጋው ላይ ወጣ…..እና ቆመ….‹‹ምነው ቁጭ በል እንጂ››

የለበሰውን ቁምጣ ከነፓንቱ አንድ ላይ መዥርጦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….እንደሀውልት የተገተረው እንትኑ አይኗቾን ተቆጣጠረ…..የበለጠ በፍርሀት ተንዘረዘረች፡፡

‹‹ምን እየሰራህ ነው?››

‹‹እንዴ ምን ሰራለሁ.. ልንተኛ አይደል ….?ብርድልብሱን እና አንሶላውን ገለጠና ከውስጥ ገባ…

.‹‹አውልቀሽ ወደእኔ ትመጪያለሽ ወይስ…..?››

ምንም መናገር አልቻለችም….ዝም አለች፡፡‹‹ምንም ልምድ የለሽም አይደል?››ሲል ጠየቃት፡፡፡

‹‹ልክ ነህ። በዚህ ረገድ ብዙ ልምድ የለኝም። እንደውም እውነቱ ለመናገር  እኔ ምንም አይነት ልምድ  የለኝም ›› አለችው ። ማስመሰል ምን ፋይዳ አልነበረው? ከአመታት በፊት ካጋጠማት ከዛ አስጸያፊ ምሽት ገጠመኞ በኋላ በእድሜ ጨምራ እና  በስሜት ጎልምሳ ሊሆን ይችላል… ግን ያ በቂ አይሆንም። ለዛውም እንደ ዘሚካኤል አይነት ከሴት ጋር ባለው ልምድ የበለፀገ አይነት ሰውን ለመቋቋም ፈጽሞ እንደማትችል እርግጠኛ ነች፡፡

‹‹ከብዙ ልምድ ያላቸው ሴቶች ጋር ተኝተሀል ..እና ከእኔ ጋር  በምታደርገው ነገር  ቅር መሰኘትህ  አይቀርም ፣ ››ብላ ጨረሰች ።ሙሉ በሙሉ ተሸነፈች።

‹‹ ውዴ ፣ ስለ እንደዛ አይነት ነገር ፈፅሞ  መጨነቅ አያስፈልግሽም -ሁሉን ነገር አብረን በዝግታና በትግስት እናደርገዋለን….እኔ አንቺን ከማንም ጋር ላወዳድርሽ ሀሳብ የለኝም….››  የእሱ አጽናኝና አበረታች ቃላት  ጉዳቷን እና ውርደቷን ትንሽ አጠበላት።ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይህ ፈተና አይደለም.›› ጎተተና ወደውስጥ ስቦ አስገባት፡፡ከዛ ቀስ አለና ቲሸርቷን ወደላይ ስቦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….ከዛ ወደኋላ አጋዳማትና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡

‹‹እንግዲህ እጅ ሰጥቻለው…ችግር የለውም ካልክ….እንደፈለክ አድርገኝ››በማለት ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠቷን በይፋ አወጀች፡፡

‹‹ ውዴ አፈጻጸም ላይ  ጭንቀት ካለብሽ ለምንድነው ለተወሰነ ጊዜ  ሂደቱን የማትመሪው?››የሚል አስገራሚ ሀሳብ አቀረበላት፡፡

በድንገት መተንፈስ አቃታት።

‹‹ትቀልዳለህ እንዴ..?ጭራሽ መምራት…‹‹በል የምታደርገውን እንደፈለግክ  አድርግ፡፡››አለችው፡፡

‹‹ደግሞ እኔም አንቺ የምታስቢውን ያህል  ጎበዝ ላልሆን እችላለው ›› ብሎ ቀጠለ፣ በብልህ ጣቶቹን ጡቷቿን እያፍተለተለ ነው፡ ፡ቃተተች፡፡እሱ ሹክሹክታ በመሰለ ድምፅ መናገሩን ቀጠለ፡፡

ተንቀጠቀጠች፡፡ከአንገቷ ጀምሮ ወደታች ይልሳት ጀመር …ሳታስበው ሰውነቱ ላይ ተጣበቀችበት….ከታች እንትኑ ክፉኛ ቆረቆራት..ደስ የሚል መቆርቆር….የሚበላ እና ሚያሳክክ አይነት መቆርቆር …እሱም እንደተመቻት ስለገባው ይሰመስላል… በጠንካራ ጡንቻው  ሰቅስቆ ወደራሱ አጥብቆ መሳሙን ቀጠለ….እያንዳንዷ የሚስማት ቦታ ልዩ አይነት የተለያየ ጣእም ያለው መስሎ ተሰማት…..ለዘመናት እንደዛ እየሳማት እንዲቆይ ተመኘች….እየቀለጠች ነው….ሆዷና ጀርባዋ በላብ እየታጠበ ነው፡፡እጁን ወደታች ሰደደና በለበሰችው ቁምጣዋንና ፓንቷን ሰቅስቆ ገባ……..‹‹ወይኔ ጉዴ ምን ሊያደርግ ነው?››አሰበች …የእጁን መዳፍ ብልቷ ላይ አሳረፈ……ድምፅ አውጥታ ማቃሰት ጀመረች….ከላዮ ላይ ተነሳና ቀና ብሎ የለበሰችውን ቁምጣን ፓንቷን አንድ ላይ ይዞ ወደታች ጎትቷ ማውለቅ ጀመረ…እግሯን ወደላይ ከፍ በማድረግ ተባበረችው፡፡ወደ ሰውነቱ አጥብቆ አቀፋትና  ከጆሮዋ አንስቶ አንገቷን መሳም ጀመረ….ተቁነጠነጠች፡፡ቀስ እያለ መሳሙንም መዳበሱንም ሳያቋርጥ ወደታች ሄደ… ከዛ አንገቱን እግሯቾ መካከል ደፈቀ….ለፈለፈች….በመላ ሰውነቷ ቤንዚል ተርከፍክፎ ክብሪት የተጫራባት ነው የመሰላት…እጆቾን ፀጉሩ ላይ አድርጋ ታሻሸው ጀመር…ቀስ አለና እየሳማት ወደላይ መጓዝ ጀመረ…  ከንፈሯ ጋር ሲደርስ ቀድማ ተጣበቀችበት….ሙሉ በሙሉ እግሮቾን መካከል ገብቷ ተዋሀዳት….ልዩ ጣፋጭነት ያለው ስቃይ ተሰማት…ስቃዩ እንዲያቆም ግን ፈፅሞ አትፈልግም…ይበልጥ  መቃተት ይበልጥ መሰቃየት ፈልጋለች፡፡ሁለቱም እኩል ከፍተኛ ፍንዳታ ላይ ደረሱ አደኛው ሌለኛውን ወደራሳቸው ጨምቀው አቀፉ..ተርገፈገፉ…..በመከራ ተላቀቁና ጎን ለጎን ተዘረሩ፡፡

ከተወሰኑ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ወደእሷ ዞረና‹‹እንዴት ነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹አረ…እንዲህ አይነት ጉብዝና መኖሩን እራሱ የት አውቃለው?››አለችው፡፡

ግንባሩን ወደ እርስዋ አስጠጋ ፣በረጅሙ  ተነፈሰች።‹‹የእኔ ቆንጆ ሁለነገርሽ እንደሚያምር ታውቂያለሽ አይደል?...አይዞሽ ሁሉ ነገር ልዩ ይሆናል…ወደፊት ብዙ የምትማሪው ነገር ሊኖር ይችላል›› አላት፡፡
#አላገባህም


#ክፍል_አስር


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

ፀደይ  በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ  ጠረን  ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ  ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን  ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን  በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡

…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና  ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።

ዛሬ  አዲስአለም እና  ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ  አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ  ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡

አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡

ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡

መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/

አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/

ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል

ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል  ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››

የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››

ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት  እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡

ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው  መጡበት፡፡

ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ  ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››

‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››

‹‹እሺ አናግረኝ…

‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››

‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን  ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡

‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››

‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››

‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡

‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››

‹‹ጓደኛሽ?››

‹‹ማ ፀዲ››

‹‹አዎ…››

‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን  ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››

‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››

‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››

‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››

‹‹ወደእናቷ ጋር፡››

‹‹በይ እንቺ ደውይላት››

‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››

‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

/////

ሚካኤል ከኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች ከፍተኛ ኃላፊ ጋር ሚስጥራዊ ስብስባ እያደረገ ነው፡፡እኚን ባለስልጣን ለማግኘትና ለማናገር በጣም ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፏል …በጣም ብዙ ገንዘብም ከስክሷል፡፡

‹‹እሺ አቶ ሚካኤል እንዳገኝህ ያሳመነን ወዳጄ ትልቅ ባለውለታዬ ነው ..ምን እንዳደርግልህ ነው የምትፈልገው?፡፡››ሲል ቦርጫቸውን እሻሹ ጠየቁት፡፡

‹‹ያው ጫፉን ያውቁታል ስለአባቴ ጉዳይ ነው››

‹‹እሱን ሰምቼለው…አባትህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሰው ነው፡፡ምን እንድረዳህ እንደፈለክም ያልገባኝ ለዛ ነው፡፡ታውቃለህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ፍርደኛ ቀጥታ ፋይሉ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ጋር ነው ሚላከው..እሳቸው ሲፈርሙበት የሞት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል…እስከዛው በእስር ይቆያል…ማንም ሰው ምንም ማድረግ አይችልም፡፡››

‹‹አውቃለው…..የእኔ ፍላጎት የሞት ፍርድ ተፈፃሚ እስኪሆንበት ያለው የማረሚያ ቤቱ አያያዝ እንዲሻሻልለት ለመጠየቅ ነው፡፡››

‹‹አዎ አንተን ለማግኘት ከመምጣቴ በፊት ስለአባትህ አጠቃላይ ሁኔታ በመጠኑ ለማጣራት ሞክሬ ነበር፡፡አሁን የታሰረው ጥብቅ በሆነ  ጥበቃ ለብቻው መሆኑን ገልፀውልኛል፡፡››አሉን ፊትለፊታቸው የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ አንስተው ተጎነጩና መልሰው አስቀመጡት፡፡

ሚካኤልም ‹‹አዎ ያስጨነቀኝ እኮ ያ ነው፡፡››ሲል መለሰላቸው፡፡

‹‹ያ ለምን እንደሆነ መቼስ ታውቃለህ፡፡አባትህ ከሌሎች በእስር ቤት ካሉ ታራሚሆች ጋር በማሰር ከማረሚያ ቤቱ ለማምለጥ ሞክሮ አንድ የፖሊስ አባልና ሁለት እስረኛ ሞተዋል፡፡የዛ ኦፕሬሽን ዋናው ማስተር ማይንድ እና መሪ ደግሞ አባትህ ነበር…ያ ውሳኔ የተወሰነበት ከዛ ክስተት በኋላ ነው፡፡ለፖሊስ መገደል ምክንያት መሆን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መገመት አይከብድህም››

‹‹አዎ አውቃለው…ግን እኮ በጣም ተቀጣ..እዛ ጨለማ ክፍል በሰንሰለት ተጠፍሮ መኖር ከጀመረ ስድስት ወር አለፈው፡፡እሺ ብቻውን ይታሰር….ቢያንስ ከጨለማ ክፍል የሚወጣበትና  ከሰንሰለት እስርም የሚገላገልበት እድል ቢኖር፡፡ዋናው ከሰው እንዳይቀላቀልና ተመሳሳይ አይነት የማምለጥ ሙከራ እንዳይሞክር አይደል››ሲል በንግግሩ ቃናም በአይኖቹም ተማፀናቸው፡፡

‹‹ይመስለኛል ..ያም ብቻ አይደለም..በእሱ ምክንያት የሞተው ፖሊስ በወህኒ ቤት ውስጥ በፖሊስችም ሆነ በእስረኞች በጣም ተወዳጅ ስለነበረ….በጓደኞቹ ዘንድ ከፍተኛ ብስጭት ፈጥሯል….እና አንድም በጣም እንዲቀጣ ይፈልጋሉ በሌላ ጎኑም በተግባሩ በተበሳጩ ሰዎች ጥቃት እንዳይደርስበትም ስጋት ስላለ መጠበቅ ይፈልጋሉ፡፡››

‹‹‹አውቃለሁ…ያ ጉዳይ በመፈፀሙ እኔም ከፍተኛ ልብ ስብራት ደርሶብኛል ፣ የሞች ፖሊስ ቤተሰቦች አግኝቼ ለማነጋገር ሞክሬለው፡፡ባለቤቱንና አንድ ልጁን ወዲው ነበር ያገኘዋቸው….እና ምንም እንኳን እሱን መልሼ ላመጣላቸው ባልችልም በኑሮ ግን እንዳይቸገሩ የተቻለኝን እያደረኩ ነው፡፡ለሚስቱ ስራ እንድታገኝ አድርጌለው….የልጁንም ትምህርት ቤት ክፍያ  እና አንዳንድ ወጪዎች እየከፈልኩ ነው….ምንም ሆነ ምንም ወደፊትም ያንን ማድረጌን አላቋርጥም፣እባኮት እርሶ በተቻሎት መጠን ይርዱኝ…ምንም አይነት ቤተሰብ እንዳይጠይቀውም ስለተከለከለ እኔ እንኳን ካየሁት ስድስት ወር አልፎኛል…››

‹‹በእውነት እያደረከው ስላለ ነገር ምስጋና ይገባሀል..ትልቅ ሰው ነህ!!እንግዲህ እንዲህ እናድርግ….አንድ አስር ቀን ስጠኝ  እና ሁኔታውን በተሻለ ሁኔታ ላጥና..ከዛ ሌሎች ጓደኞቼንም ቢሆን አስቸግሬ ማድረግ የምችለውን ነገር ላስብበትና መልሰን እናውራበት››

‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው…..ምን አልባት ጓደኞቾትን ሲያስቸግሩ የሚያስፈልግ ነገር ካለ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አሟላለሁ…፡፡››ሲል ቃል ገባ፡፡

‹‹ችግር የለም… የሚስፈልግ ነገር ካለ አሳውቅሀለው….እነደነገርኩህ አንተን እንድረዳህ የጠየቀኝ ሰው በጣም ወዳጄና ባለውለታዬ ነው…..እና በእኔ አቅም ማድረግ የምችለውን ነገር ሁሉ እንደማደርግና የአባትህን በእስር ቤት ውስጥ ያለውን አያያዝ ለማሻሻል ጥረት እንደማደረግ ልገልጽልህ አፈልጋለው…በተለይ አባትህን የመጠየቅ  መብትህን መልሰህ እንድታገኝ ማድረግ ምችል ይመስለኛል፡፡››

‹‹አመሰግናለው..ስልኮትን በጉጉት ጠብቃለው፡፡›› በዛው ተለያዩ
////
ፀአዳ  በአራተኛው ቀን ስሜቷን አብርዳ….መረበሿን አረጋግታ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ከዶዶላ ተመልሳ አዳማ እስክትገባ ስልኳን አልከፈተችም ነበር፡፡ቤቷ ደርሳ አረፍ እንዳለች ከፈተችና ለአዲስ አለም ደወለችላት፡፡

አዲስአለም ከሰላምታ ሳይሆን ከስድብ ነው የጀመረችው‹‹አንቺ ቅሌታም…..ጤነኛ ነሽ ግን?››

‹‹ቀስ …ይሄ ሁሉ ቁጣ ናፍቆት ነው ወይስ ሌላ ምክያት አለው?፡፡››

በስድቧ ገፋችበት ‹‹ወሬኛ ነሽ እሺ…..ለመሆኑ አሁን የት ነሽ?››

‹‹ቤቴ ነኛ››

‹‹ማለት እዚህ አዳማ?››

‹‹አዎ..ምነው ሌላ ቦታ ቤት አለኝ እንዴ?››

‹‹እኔ ምን አውቅልሻለው….ግን ሳስበው በቅርብ አዲስአበባ ላይ ቤት የሚኖርሽ ይመስለኛል….በቃ ጠብቂኝ አሁኑኑ መጣሁ…፡፡››

‹‹ኸረ እኔ ራሴ መጣለሁ…፡፡››

‹‹መጣው እኮ አልኩሽ፡፡››ስልኩን ጠረቀመችባት፡፡

‹‹ዛሬ ልትደበድበኝ ሁሉ ትችላለች››ስትል አሰበችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ማስተካከል ጀመረች ..ተዘግቶ ስለከረመ እምክ እምክ ይላል…መስኮቱን ከፋፈተች…ሰንደል ለኮሶችና በየኮርነሩ ላይ ሰካካች… ቡና ለማፍላት ሲኔ ደረደረች፣ከሰል በማቀጣጠል ላይ እያለች አዲስ አለም መጣች፡፡

ጠየቀቻት ካሰበችው ጊዜ በጣም ፈጥና በመምጠቷ ተገርማ‹‹እንዴ ..!!ስትደውይልኝ መንገድ ላይ ነበርሽ እንዴ?››ስትል ….፡፡
ልትስማት ስትጠጋት ወደኃ ሸሸቻትና ገፍትራት ወደቤት ገባች….ፀአዳማ እያቀጣጠለች የነበረውን ከሰል ትታ ከኃላ ተከተለቻት፡፡

‹‹ምስር የታለች?››

‹‹ጎረቤት ልትጫወት ሄዳለች››

‹‹ቆይ አንቺ ግን ያምሻል..?እንዴት አንድ ነር ሳትነግሪኝ ብን ብለሽ ትሔጃለሽ…እሺ መሄዱንስ ሂጂ እንዴትሰ ስልክሽን ትዘጊያለሽ?››

‹‹ስልኬ እኮ ተበላቶብኝ ነው››

‹‹አረ ባክሽ..አሁን እኔን የምትሸውጂኝ ይመስልሻል?››

‹‹‹እሺ በቃ ማንንም ለማውራት ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም…በፀጥታ ማሰብ ነበር የፈለኩት..በዛ ላይ አንቺ የሰርግና የመልስ ግርግር ላይ ስለሆንሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም››

‹‹ወይ ረበሺኝ እኮ..እኔን ብቻ ሳይሆን ባሌንም ጭምር ነው በደንብ የረበሺን፡፡››

‹‹እንግዲህ አዝናለው…..በጣም ይቅርታ›

‹‹ደግሞ ሰውዬሽ..አብዶልሻል….››

‹‹የቱ ሰውዬ?››ግራ በመጋባት ጠየቀች፡፡

‹‹ስንት ሰውዬ ነው ያለሽ…?ዘሚካኤል ነዋ..ከደበቅሺበት  ውለጂያት ብሎ ሊያንቀኝ››

‹‹እንዴ ደወለልሽ እንዴ?››
ምን ይደውልልኛል…በዛን ቀን ልክ ያንቺ መልእክት ደርሶኝ እሱን ከሚካኤል ጋር አንብበን እየተገረምን ሳለ ቤት ድረስ መኪናውን እያከነፈ መጣና ሰፈሩን በመኪናው ክላክስ አደበላለቀው…ምን ሆኖ ነው ብዬ ስወጣ መኪና ውስጥ አስገባኝና ከሰፈር ይዞኝ ሄደ….››ብላ የዛን ቀን የሆነውን በዝርዝር ተረከችላት፡፡›

ፀአዳ በሰማችው ነገር በጣም ተገረመች‹‹ፈፅሞ እንደዛ ያደርጋል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር…ግፋ ቢል ደውሎ የሆነ ነገር ይልሻል ብዬ ነው ያሰብኩት፡፡››

‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?ልጁ እኮ ጨርቁን ጥሎልሻል››

‹‹ማለት?››

‹‹አፍቅሯሻል እያልኩሽ ነው››

‹‹እኔ ፍቅር አልፈልግም››

‹‹እና ወሲብ ነው ምትፈልጊው?
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
ከአስር ቀን በኃላ ያሉት ባለስልጣን ከሳምንት በኃላ ደወሉለት..አልጠበቀው ነበር፡፡‹‹ሚካኤል አንድ ጥሩ ዜና አለኝ››

‹‹ምንድነው ጌታዬ?››በጉጉት ጠየቀ፡፡

‹‹ነገ ሰባት ሰዓት ላይ አባትህን እንድታገኝ  ከእስርቤቱ አስተዳዳሪ ፍቃድ አግንቼልሀለው፡፡››

‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው›..እግዜር ይስጥልኝ››

‹‹አዎ በሰአቱ ሂድና…ቀጥታ አሁን በምልክልህ ስልክ እዛ እንደደረስ ደውልለት… አስተዳዳሪው ራሱ ይቀበልህና ሚሆነውን ያደርጋል….ሌሎች ነገሮችን እየሰራሁባቸው ነው….እስከዛው በዚህ ተፅናና…››

‹‹እሺ ጌታ ..በጣም ነው የማመሰግነው››

ስልኩን ዘጋና በደስታ ዘለለ…ልጇን እያጠባች ሁኔታውን ስትከታተል የነበረችው አዲስአለም ..‹‹ምን ተገኘ..ሎቶሪ ወጣልህ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹በይው…ነገ አባዬን እንድጠይቀው ተፈቀደልኝ››

‹‹በእውነት..በጣም ደስ ይላል››

‹‹አዎ….ምንድነው ይዤለት የምሄደው…..?››ሲል ከፈንጠዝያው ሳይወጣ ጠየቀ፡፡

‹‹አንተ ምን አልባት ቅያሪ ልብስ የላቸውም ይሆናል..ልብስ ምናም አዘጋጅ..እኔ ደግሞ የሚበላ ነገር አዘጋጃለው፡፡››

‹‹ትክክል ነሽ ..የእኔ ማር በጣም ደስ ብሎኛል….››

‹‹ደስ ይላል..ግን ያው አባትህ እስር ቤት ከገቡ ጀምሮ ልትጠይቃቸው በሄድክ ቁጥር በምን አይነት አቀባበል እንደሚቀበሉህ ታውቃለህ…እንዲህ በመፈንጠዝ ሄደህ በኃላ አላናገረኝም….መጥተህ አትጠይቀኝ አለኝ…ምናምን ብለህ እንዳትበሳጭ››ስትል ስጋቷን ገለፀችለት፡፡

‹‹አረ…የፈለገ ይበል እኔ አይኑን ማየት ብቻ ነው የምፈልገው….ከፈለገ ለምን  ልትጠይቀኝ መጣህ ብሎ በቡጢ  አይነርተኝም ..ግድ አይሰጠኝም››

አሳዘናት…‹‹ሁሉም ሰው ምናለ እንዳአንተ ሰው ወዳጅና ሌላውን የሚረዳ ቢሆን››ስትል በውስጦ አሰበች‹አይ እንደዛ ከተዘጋጀህ ጥሩ››አለችው፡፡

‹‹በቃ ወጣው ….በዛው ለአባዬ የሚሆን ልብስ ገዛዛለሁ››ብሎ ሚስቱን ጉንጯን ልጁን ግንባሩን ሳመና ወጥቶ ሄደ፡፡

ሚካኤል ለአባቱ ልብስና የሚበሉ የተለያዩ ትኩስ  ምግቦችን ተሸክሞ ልክ በተባለው ሰዓት ወህኒ ቤት ጊቢ ደርሶ ስልኩን ደወለ፡፡

‹‹ሄሎ ኩማንደር …ሚካኤል ነኝ…ቀጠሮ ነበረኝ፡፡››

‹‹እ ሚካኤል ….ጥበቃ ላይ ካሉት ፖሊሶች አስርሀለቃ ላቀው በልና ንገረው …ነግሪዋለው ወደእኔ ይዞህ ይመጣል፡፡››የሚል አስደሳች መልስ አገኘ፡፡

‹‹እሺ ኩማንደር አመሰግናለው››
ስልኩን ዘጋና ፊት ለፊቱ ያለውን ፖሊስ ‹አስር ሀለቃ ላቀውን› እንዲያሳየው ጠየቀው….እዛው በቅርብ የነበረ ፖሊስ ጠቆመው፡፡ማንነቱን ለፖሊሱ ነገረና ..ለአባቱ ይዞ የመጣውን እቃ እንዲያስረክ ካደረገ በኃላ ቀጥታ ወደኮማንደር ቢሮ ይዞት ሄዳ፡፡ፖሊሱ ክፉሉን ቆርቆሮ ከፍቶ አስገባውና መልሶ ሄደ፡፡

ሲገባ  የገጠመው ግዙፍና ግርማ ሞገስ ያለው ቢሮ ነው፡፡እዚህ ቀፋፊ ወህኒ ቤት ውስጥ እንዲህ አይነት የሚያምር ቢሮ ይኖራል ብሎ ገምቶ አያውቅም፡፡ፀጉራቸው ሙሉ በሙሉ ቀለሙን ቀይሮ ነጭ የሆነው   ግዙፉ ጠይም ቆፍታምና ሰው ከግዙፉ ጠረጴዛ ኃላ ባለ የቆዳ ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጠው ይታያሉ….በጎርናና እና ሻካራ ድምጻቸው ‹‹ግባ አቶ ሚካኤል…..››አሉት

ሄደና ወደእሳቸው ቀርቦ ለሰላምታ እጁን ዘረጋላቸው…በመጠኑ ከመቀመጫቸው እንደመነሳት አሉና እጃቸውን ዘርግተው ጨበጡትና‹‹ተቀመጥ አቶ ሚካኤል›

እሺ ብሎ አንዱን ወንበር ሳበና ተቀመጠ‹‹ኩማንደር ስለአስቸገርኩት ይቅርታ….ያው የቤተሰብ ጉዳይ  ስለሆነብኝ ነው››ሲል  ተናገረ፡፡

‹‹ይገባኛል…እንደውም ጥሩ ልጅ ስለሆንክ መመስገን አለብህ…መቼስ ማረሚያ ቤታችን በአባትህ ላይ የወሰደው አቋም ለምን እንደሆነ ይገባሀል አይደል?አዎ ይገባሀል እንጂ …በእኛ ልትበሳጭ ፍፅም አትችልም፡፡››

‹‹አዎ በትክክል ይገባኛል….››ሲል በአጭሩ መለሰ፡፡

‹‹አሁን ያው ከአንተ ጋር እየተነጋገርን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን ሁኔታዎችን ለማስተካከል እንሞክራለን….ዋናው አንተ አባትህንን  ምን ያህል ?ማገዝ ትፈልገለህ የሚለው ነው››አሉና ፈገግ ብለው በሲጋራ የበለዘ ጥርሳቸውን አሳዩት፡፡

‹‹ኮማንደር አባቴ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት መሞቻ ቀኑን የሚጠብቅ ሰው ነው…እና ያ ቀን አስኪደርስ ድረስ  በተቻለ መጠን በተመቻቸ ሁኔታ እንዲያሳልፍ ማንኛውንም ነገር ለማድረግ ፍቃደኛ ነኝ፡፡አባቴ ይሄንን ቀፋፊ ወንጀል ሰርቶ ወህኒ ቤት ከመግቱ በፊት ለቤተቡ አይደለም ቸገረኝ ላለ ሰው ሁሉ ልብ የሚያዝንና እጁ የሚፈታ መልካምና የተከበረ ሰው ነበር…..ምንም ሆነ ምንም ፍፃሚዊ እንዲህ አሳዛኝ መሆን የለበትም፡፡

‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ ማድረግ ይምንችለውን ሁሉ እናያለን፡፡››አሉን ወደፊት ተንጠራርተው መጥሪያውን ተጫኑ..አንድ ፖሊስ መጣና ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠ…‹‹ሳጂን  ታራሚ ቅጣውን እዚህ አስመጣልን››ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡ
ፖሊሱ ትዕዛዙን ተቀበለና ተመልሶ ወጥቶ ሄደ….ከ5 ደቂቃ በኃላ እስከአሁን ያለሳተዋለው በኩማንደሩ መቀመጫ በቀኝ በኩል የምትገኝ ጠበብ የጀርባ በራፍ ተቆረቀረ…ኮማንደሩ ዝርጥት ሰውነታቸው እየከበዳቸው በመከራ  ተነሱና በራፉ ከውስጥ ከፍተው ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ አይኖቹን የተከፈተው በራፍ ላይ እንደተከለ መጠበቅ ጀመረ…ሰው ከማየቱበፊት ብረት ቅጭልጭልታ በጇሮው ሞላ..…ከዛ በተቀመጠበት ደንዝዞ ቀረ..አባቱን ከስድስት ወራት በፊት ነው ያየው…ሰው በስድስት ወር በዚህ መጠና ሊቀየር እንደሚችል ግምቱ የለውም ፡ፀጉሩ ተንጨፍርሮ ተንጨፍርሮ ጉድሮ ሆኖ ግንባሩ ላይ ተደፍቷል…ፂሙ አድጎ ግማሽ ፊቱን ሸፍኖት ያረጀ አንበሳ አስመስሎታል…ከመክሳቱ የተነሳ ሁለቱ ጉንጮቹ አንድ ላይ የተጣበቁ ይመስላል፡፡አይኖቹ ጥልቅ ጉድጓዱ ውስጥ ያሉ ደማቅ አንፖሎች ነው የሚመስሉት…ሚካኤል እንባው ዝርግፍ አለ..ኮማደሩ ከተቀመጡበት ተነሱና ..ለብቻችሁ ጊዜ ልስጣችሁ..አንድሰዓት አላችሁ……በፊት ለፊተኛው በራፍ   ክፉሉን ለቀውላቸው  ወጡና  ከውጭ ቀርቅረውባቸው ብቻቸውን ተዋቸው…
እንደምንም እራሱን አበረታቶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደአባቱ ሄደ…ልጅ እያለ ባለግርማ ሞገሳሙ አባቱ  ወደ ቤት መምጣቱን የሚያውቀው የመኪናውን ክላክስ ሲሰማ ነበር..ካዛ ከወንድሙ ጋር ሮጠው ከቤት ይወጡና  ወደእሱ ይንደረደራሉ…ከዛ ለልጆቹ የገዛላቸውን ፍራፍሬ ወይም ሌሎች ጣፍጭ  ነገሮች የያዘ ፔስታል ይዞ ከመኪናው ሲወርድ እሱን ጨምሮ ሶስቱም ልጆቹ በሽሚያ አንዱ ቀኝ እግሩን ሌላው ግራ እሩን ያቅፍትና በልዩ ፈንጠዝያ ይቀበሉታል…እሱም ስራቸው ይንበረከክና አንዱን ጉንጩን ሌላዋን ግንባሩን እያሳመና እየዳበሰ ይዞቸው ወደቤት ይገባል…አባትዬው ለልጆቹ እንስፍስፍ የሚባል አባት ነበር..በተለይ  ዬቱ ታላቅ የሆነችውን ሴት ልጁን በልዩነት ንው የሚወዳት…እሷም በአባቷ በምንም አይነት ሁኔታ የማትደራደር  የእሱ ተመራጭ ልጅ ነበረች…እና እንደዛ ኩሩና ሽቅርቅር የነበረው አባቱ አሁን አፅሙ ብቻ ነው ያለው..ሄዶ በፍራቻ ተጠመጠመበት.. ጠረኑ ወደኃላ ይገፋተራል…አባትዬው ምንም አይነት ምላሽ አላሳየውም..እየጎተተ ወደወንበሮቹ ወሰደውና አስቀመጠውና ከፊት ለፊቱ ተቀመጠ፡፡

‹‹አባዬ እንዴት ነህ?››

ለእሱ መልስ ከመስጠት ይልቅ ‹‹ለምን እንደዚህ አደረክ?››ሲል አንቧረቀበት፡፡

‹‹ማለት? ምን አደረኩ?››ምን ስህተት እንደሰራ ባለማወቅ በፍራቻ ጠየቀ፡፡

‹‹ለምን አገኘኸኝ..?እንዴት እንደተቀጣሁና ምን አይነት ቀፋፊ አውሬ እንደሆንኩ ለማየት ነው የመጣኸው?››
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
ሚካኤል ከወህኒ ቤት እንደመጣ ቀጥታ ወደሰፈር ነው ያመራው፡፡ወደቤት ሲገባ አዲስ አለም ከልጇ ጋር እየተዳረቀች ሳሎን ውስጥ ቢያገኛትም ማንኛቸውንም ምንም ሳያናግር ቀጥታ ወደመኝታ ቤት ነበር የተንደረደረው፡፡

‹‹ሚኪ…ምን ሆነሀል.?.ዛሬ ደግሞ ሰላምታ የለም እንዴ?››

‹‹መጣሁ..››ብሎ ብቻ  ወደመኝታ ቤት ገባ…አባቱ የነገሩትን ፎቶ ከግድግዳ ላይ አነሳ ..ከግድግዳው ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ነው…በቀላሉ በእጅ የሚፈረከስ አይነት አይደለም…ከእንደገና ተነደርድሮ ወጣና በጓሮ በኩል ወደ ገራጅ በመሄድ መዶሻ እና መሮ  ይዞ መጣ….‹‹አዲስ አለም ቅዱስን ከወለሉ ላይ አንስታ አቀፈችውና ወደመኝታ ቤቱ ተንቀሳቀሰች…እሷ ከመድረሷ በፊት ሚካኤል ወደውስጥ ገብቶ ከውስጥ ዘጋባት

‹‹እንዴ ሚኪ….ምን እየሆንክ ነው…?ለምንድነው የምትዘጋብን?››

‹‹አዲስ..እባክሽ ጥቂት ደቂቃዎችን ስጪኝ……››ብሎ መሮውንና መዶሻውን በመጠቀም  ግድግዳውን መቆርቆር ጀመረ…ግድግዳ ውስጥ የተቀመጠውን የአባቱን ሚስጥራዊ እቃ ለማግኘት 3 ደቃቃ ያህል ፈጀበት…በላስቲክ በስነሰርአት የተጠቀለለ ነው፡፡አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠና የላስቲኩን እሽግ ፈቶ አልጋው ላይ ዘረገፈው፡፡….አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች አንድ ሜሞሪ ካርድ  ..አንድ ደብዳቤ ነው፡፡፡

መጀመሪያ ፎቶዎቹን አነሳና ተራ በተራ መመልከት ጀመረ…የመጀመሪያው ፎቶ ላይ  አናትዬው የሆነ ሰው ክንድ ላይ ተደግፋ በፈገግታ ስትፍለቀለቅ ይታያል..ጭንቅላቱን የሆነ መርፌ ነገር ጠቅ አደረገው….ይሄ ሰው በህይወት ዘመኑ አይቶት አያውቅም…የእናቱን ዘመዶች ሁሉንም ያውቃል…ታዲያ ይሄ ማን ነው?፡፡ሁለተኛውን ፎቶ  ገለጠና ተመለከተ…እናትዬው እነሱን ከመውለዷ በፊት ገና ጨቅላ ወጣት ሆና የተነሳቸው ፎቶ ነው..ግን አሁንም ያው ሰው አንገቷ ላይ ተጠምጥሞ በፍቅር ጉንጯን ሲስማት ይታያል…ፎቶውን ገለበጠው…ልቅም ባለ የእጅ ፅሁፍ በአንድ መስመር የተፃፈ ፅሁፍ አለ ‹‹ንጥፍ ወርቅ ፍቅሬ በጣም አፈቅርሻለው….ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡››ይላል፡፡
ሁሉንም ፎቶዎች በየተራ እየገለባበጠ ተመለከተው…ተመሳሳይ የሁለቱ ፎቶ ነው…ሲላፉ ሲሳሳሙ….ሲጎራረሱ የተነሱት ፎቶ ነው፡፡
ቤታቸው የወላጆቻቸውን ትዝታ የሚዘክሩ ሁለት ግዙፍ የፎቶ አልበሞች እዳሉ ያውቃል….እናትና እህቱ በአሰቃቂ ሁኔታ ከሞቱ በኃላ በጣም ሲከፋውና ትዝ ሲሉት ለብቻው ክፍል ዘግቶ ተደብቆ  ይመለከት ነበር፡፡እና እዛ አልበም ውሰጥ ዘጠና ፐርሰንት ፎቶ የእሱና የእህትና ወንድሙ ፎቶዎች ፤የበዓል ዝግጅት ፤ የህፃናቱ የልደት በዓል ማስታወሻ ናቸው የሞሉት..እናትና አባቱ በልጆቹ የደስታ ድባብ ውስጥ እንደድምቀት እዚህም እዛም ጣል ተደርገው የተነሱት ነው እንጂ እንዲህ እናቱ ከሌላው ሰውዬ ጋር እንዳደረገችው አይነት አማላይ ፎቶዎች ተነስተው አላየም፡፡

ፎቶውን አስቀመጠና ወረቀቱን አንስቶ አነበበው…
ይድረስ ለምወድሽ ፍቅሬ ንጥፍ ወርቅ …
ይህንን ደብዳቤ ስፅፍልሽ ከአይኖቼ እንባ ሳይሆን ደም እያፈሰስኩ ነው፡፡  ታውቂያለሽ እኔ ከኤለመንተሪ ጀምሮ በጣም ነው የማፈቅርሽ..አንቺም እንደምታፈቅሪኝ አውቃለው፡፡ብዙ አቅድና ብዙ ፕሮግራም ነበረን፡፡በቅርብም ለመጋባት ተነጋግረንና ተማምለን ነበር፡፡አሁን ግን ያንን ቃሌን ማክበር አልችልም፡፡አባዬ ምን ያህል ኃይለኛ እና ጥብቅ ሰው እንደሆነ ታውቂያለሽ  ..አሁን አሜሪካ ካለው ወንድሙ ጋር ተነጋግሮ አሜሪካ እንድሄድ ወስኖ ሁሉም ፕሮሰሶች ጨርሶ ሊልከኛ ነው…ማለቴ… አሁን ይሄ ደብዳቤ ሲደርስሽ ምን አልባት እኔ በርሬም ሊሆን ይችላል፡፡

ይቅር በይኛ…..ያንቺው  ለሚ በቀለ፡፡ይላል
እዛ ደብዳቤ ላይ ብዙ የተንጠባጠቡ የእንባ ጠብታዎች ይታያሉ፡፡ሚካኤል ያየውም ሆነ ያነበበው ነገር  ምንም እየገባው አይደለም..ከውጭ ደግሞ አዲስአለም የመኝታ ቤቱን በራፍ እየቆረቆረች እየረበሸችው ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ሄዶ በራፉን ከፈተ፡፡ በራፉ ላይ ልጇን አቅፋ ተገተትራ በድንጋጤ በድን የሆነችውን አዲስ አለም ላይ አፈጠጠባት፡፡

‹‹አዲስ ምንድነው?››

‹‹እንዴት መኝታ ቤቱን በላይህ ላይ ዘግተህ ምን እያደረክ ነው?››በስጋትና በፍራቻ ተወጥራ ጠየቀችው፡፡

‹‹ኡፍ …ስራ ይዣለሁ ስልሽ አትሰሚም…..ባክሽ አትረብሺኝ››በማለት አንቧረቀና መልሶ ዘጋባት፡፡ከዛ  ወደአልጋው ተመለሰ፡፡አዲስአለም በመጀመሪያ ከደነገጠችውን  በላይ ደነገጠች…ሚካኤል ምንም ባልገባት ነገር እንዲህ አመናጭቋት አያውቅም፡፡

ወደሳሎን ተመለሰችና ፀአዳ ጋር ደወለችላት፡፡
ስታወራ ድምፃ ይንቀጠቀጣል‹‹ሄሎ ፀዲ..አሁኑኑ ወደቤት ነይ››
‹‹እንዴ ምን ሆንሽ..?

ቅዱስ አመመው እንዴ?››
‹‹አይደለም..አባትዬው ነው፡፡››

ፀአዳ በጣም ደነገጠች‹‹እንዴ  ሚኪ ምን ሆነ?››

‹‹እኔ እንጃለት… ቅድም አንቺ ጋር የመጣሁ ጊዜ አባቱን ለመጠየቅ ወህኒ ቤት ሄዶ ነበር…ከዛ ሲመለስ እንደእብድ አድርጎት መኝታ ቤቱ ገባ..ከዛ ወጣና መዶሻና መሮ ይዞ ገብቶ በራፉን ከውስጥ በመዝጋት ግድግዳውን ሲነድለው ነበር…አንኳኩቼ ምን እንደሆነ ስጠይቀው አጓርቶብኝ መልሶ ዘጋው…እህቴ ቶሎ ድረሺኝ…የቀትር ጂኒ ሳያጠናግረው አይቀርም››

‹‹ስለአባቱ መጥፎ ነገር ሰምቶ ይሆን እንዴ?››

‹‹መሰለኝ….ወይ በፈጣሪ ምን አልባት እዛ ሲደርሰ ገድለዋቸው እንዳይሆን ነው የምፈራው..እንደዛ ቢሆንስ በራፍ አስዘግቶ ግድግዳ ያስንዳል እንዴ…?››

‹‹በቃ መጣሁ ..እስከዛው ተረጋጊ››አለቻትና ስልኩን ከመዝጋቷ በፊት ቦርሳውን አንጠለጠለችና መንገድ ጀመረች፡፡

ሚካኤል ሜሞሪውን አነሳና ስልኩ ውስጥ ከተተው፡፡ሁለት ፎልደሮች  አሉት፡፡አንደኛውን ከፈተ ….በምስሉ በቅድሚያ ምትታየው እናቱ ነች፡፡አዎ ቡቲክ ቤታቸው ውስጥ ሆና ልብሶችን ሰታስተካከል ይታያል…ወዲያው አንድ በእሷ እድሜ ያለ ሰው  መጣ …የሰውዬው ጀርባው ነው ሚታዬው እናትዬው ግን በሰውዬው መምጣት ስትደነግጥ ይታያል፡፡

‹‹ለሚ እንዴት መጣህ?››አገላብጣ እየሰማችው ትጠይቀዋለች፡፡

‹‹እንዴት መጣህ ነው እንኳን ደህና መጣህ ነው የሚባለው?እዚህ ስብሰባ ነበረን …ሳላይሽ ተመልሼ መሄድ አልቻልኩም›››

‹‹እንዴ ከሶስት ቀን በኃላ ቀጠሮ ነበረን እኮ…››

‹‹እሱም እንዳለ ነው…ግን እኔ እኮ በየቀኑ ላገኝሽ ነው የምፈልገው…እንደውም ሙሉ በሙሉ የእኔ እንድትሆኚ ነው የምፈልገው፡፡››

‹‹እሱንማ አስረግዘኘኝ  ጥለኸኝ አሜሪካ ከመሄድህ በፊት   ማሰብ ነበረብህ፡፡››

‹‹ይሄንን እኮ ብዙ ጊዜ  ተነጋግረንበት  ሁኔታውን አስረድቼሽ ይቅር ብለሽኛል..አይደል እንዴ የእኔ ፍቅር?››

‹‹አዎ ግን …ይቅር አልኩህ ማለት ለአመታት የገነባሁት ትዳሬንና ልጆቼን በትኜ ወደአንተ ለመመለስ እፈልጋለው ማለት አይደለም፡፡››

‹‹ልጆችሽን በትኚ አልልኩም እኮ ….ባልሽን ፍቺና ልጆቹን ይዘሽ ነይ ነው፡፡›››

‹‹አይ ያንን ሳደርግ ቅጣው እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ይመስልሀል….?እሱ ምንም እንከን የማይወጣለት ድንቅ አባትና ምርጥ ባል ነው፡፡ልጆቹን እንዴት እንደሚወድ እና እንዴት እንደሚንከባከብ ብታውቅ እንዲህ ለማለት አትደፍርም..በተለይ ትርሲትን በልዩ ሁኔታ ነው የሚወዳት…ሲጠራት እኮ እናቴ ነው የሚላት…እሷስ ብትል..?››

‹‹ግን እውነተኛ ልጁ አይደለችም…ትርሲት የእኔ  ልጅ ነች፡፡››

ሚካኤል በሚሰማው ነገር ሆዱ ሲገለባበጥ ይታወቀዋል…አረ እንደውም ሊያስታውከው እየተናነቀው ነው፡፡

‹‹አረ ድምጽህን ቀንስ..ድንገት ሰው ቢሰማህስ?››
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////

ሚካኤልና ፀአዳ አንድ ሬስቷራንት ቁጭ ብለው ተፋጠዋል፡፡ከሁለቱም ፊት ለፊት ተከፍቶ የተቀመጠ ቢራ አለ..አንዳቸውም ግን አንስተው አልተጎነጩለትም፡፡

‹‹ለምን ጊዜችንን ትጨርሳለህ…የሆንከውን ካልነገርከኝ እንደማለቅህ ታውቃለህ››

‹‹ፀዲ..ለምን ችክ ትያለሽ..?ምንም አልሆንኩ የስራ ጉዳይ ነው አልኩሽ እኮ››

‹‹እኮ ግድግዳ በመዶሻ የሚያስነድል ምን አይነት የስራ ጉዳይ ነው?፡፡ሚኪ እኔ እኮ ለአመታት ነው የማውቀው..አንተን የስራ ጉዳይ በዚህ ልክ ሊያበሳጭህ…ኦረዲ አብደሀል እኮ››

‹‹ተይ ፀዲ አታጋኚ››

‹‹አጋነንኩ እንዴ…?የማትነግረኝ ከሆነ …››አለችና እጇን ወደ ሱሪ ኪሷ ሰዳ ስልኳን አወጣች፡፡
‹‹ምን ልታደርጊ ነው?››ግራ በመጋባት ጠየቃት፡

‹‹ብቻዬን አልቻልኩህም..ለአዲስ ደውልላትና ትምጣ..ከዛ ለሁለት እንሞክርሀለን››

‹‹በፈጠረሽ……የእሷን ጭቅጭቅና ለቅሶ የምሸከምበት ትእግስቱ የለኝም››

‹‹እና ንገረኛ››

‹‹እሺ ነግርሻለው››
ስልኩን ጠረጴዛ ላይ ከቢራ ጠርሙሱ ጎን አስቀመጠችና ሙሉ ትኩረቷን ወደእሱ አደረገች፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ቁዘማ በኋላ እንደምንም አፉን ከፈተ‹‹የአባቴ ጉዳይ ነው››

‹‹እሱንማ አውቄለው…ከዛ ውጭ አንተን በዚህ ልክ ሊረብሽ የሚችል ሌላ ጉዳይ የለም…በዝርዝር ንገረኝ፡፡

‹‹አባቴ እናቴንም ሆነ እህቴን እንዳልገደላቸው ነገረኝ…እኔም አምኜዋለው››

ፀአዳ ክፉኛ ደነገጠች‹‹እና ማን ነው የገደላቸው..?ማለቴ እንዴት ሞቱ?››ተንተባተበች፡፡

‹‹እሱን አላውቅም…አባቴ ግን ከመሞቴ በፊት እናትህንና እህትህን እኔ እንዳልገደልኳቸው በትክክለኛ ማስረጃ አረጋግጥልኝ፡፡ከመሞቴ በፊት ልጆቼ እኔ ንፅህ ሰው መሆኔን ማወቃቸውን ማረጋገጥ እፈልጋለው››አለኝ በማለት ሙሉውን ታሪክ በዝርዝር ነገራት፡፡

‹‹እና አሁን ምን ልታደርግ ነው…?እንዴት አድርህ ማረጋገጥ ትችላለህ?››

‹‹ግድግዳውን የናድኩት ለዛ ነበር..አባቴ እዛ ግድግዳ ውስጥ የደበቃቸው የተወሰኑ ማስረጃዎች ነበሩ..አለና ስልኩን ከፍቶ  በሚሞሪ ያሰቀመጣቸውን ቪዲዬዎች አስደመጣት፡፡ሽምቅቅ አለች፡፡

‹‹በጣም ያሳፍራል አይደል?››አላት፡፡

‹‹በእውነት ምን እንደምልህ አላውቅም››ስትል መለሰችለት፡፡

‹‹አየሽ ክህደት ምን እንደሆነ ምን አይነት ህመም እንደሚያስከትል ከእኔ በተሻለ አንቺ ታውቂያሽ..አባቴ እነዚህን ሁሉ መረጃዎች ካወቀ በኋላ ሚስቱ እሱን ሳይሆን ሌላ ሰው እንደምታፈቅር ከተረዳ በኋላ…በጣም የሚወዳት ቀምጥል ልጁ የእሱ ሳትሆን የሌላ ሰው ልጅ እንደሆነች ካወቀ በኃላ  ….የሁለት መንታ ወንድ ልጆቹ እናት እሱን ጥላ ወደልጅነት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ዝግጅት ላይ እንዳለች በግልፅ ካወቀ በኋላ  ምንድነው ማድረግ ያለበት?ይሄንን ሁሉ በደል እንዴት መቋቋም ይችላል…?እና  እሱ ቢቀውስና የእብድ ስራ ቢሰራ ይፈረድበታል?››

‹‹በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው…ግን እኮ አላደረኩትም ብለውሀል….›››

‹‹እሱማ  አዎ እወነቱን እንደሆነ ደግሞ እርግጠኛ ነኝ….ግን እንዳውቀው ካስቀመጠልኝ መረጃ አንድም እሱ እንዳለደረገው የሚገልጽ ፍንጭ ማግኘት አልቻልኩም..እና መተንፈስ እስኪያቅተኝ ድረስ በጣም ግራ ተጋብቻለው፡፡

‹‹ምን እንደገረመኝ ታውቃለህ?››አለች፡፡

ትኩረቱን በሙሉ ወደእሷ ሰበሰበና‹‹ምን? ››ሲል ጠየቃት፡፡
አባትህ በግድያው ተጠርጥረው ፍርድ ቤት በሚመላሰሱበት ጊዜ ይሄንን አሁን ለአንተ የሰጡህን መረጃዎች ለምን ለፍርድ ቤቱ አላቀረቧቸውም….ቢያንስ እኮ የተፈረደባቸው የሞት ቅጣት ወደእድሜ ልክ ይቀየርላቸው ነበር፡፡››

‹‹አዎ..ትክክል ነሽ…መረጃዎቹን እንዳገኘው እኔም ወደ አእምሮዬ የመጣው የመጀመሪያ ጥያቄ እሱ ነበር..እና ትናንትና ወደወህኒ ቤት ሄጄ አግኝቼው ነበር….ለምን ለፍርድ ቤት እንደመረጃ አድርገህ አላቀረብከውም ስለው…ለእናንተ ስል?››ሲል መለሰልኝ፡፡

‹‹አልገባኝም… እንዴት ለእኛ ስትል ?››ብየየ መልሼ ጠየቅኩት፡፡
‹‹እንዳልከው ይሄንን ለፍርድ ቤት እንደወንጀል ማቅለያ አድርጌ ባቀርብ ኖሮ ይሄኔ እናትም አባትም ነበር የምታጡት፡፡በወቅቱ የእኛ ቤተሰብ ጉዳይ በየጋዜጣውና መፅኄቱ እንዴት እንደሚፃፍ ታውቃለህ..ይሄ ነገር ወጥቶ ቢሆን ኖሮ ስለእናትህ ምን እንደሚፃፍ አስበው…የተፃፈ ነገር ደግሞ ታሪክ ሆኖ ይቀመጣል…የልጅ ልጇቼ ጭምር ስለወንድ እና ሴት አያታቸው ታሪክ ሲያነብ ምን አይነት የልብ መሰበር ያጋጥማቸዋል…የእኛን ማህበረሰብ ለነገሮች ያለውን ብያኔ የምታውቀው ነው..በእኔ ጉዳይ ምን ያህል ፈተና እና መገለል እንደሚገጥማችሁ አውቃለው…ይሄ የእሷ ታሪክ ቢጨመርበት ኖሮ መግቢያ መውጫ ነው የሚያሳጦችሁ››በማለት መለሰልኝ፡፡

‹‹አይገርምም !!ወላጅ መሆን እኮ እዳ ነው..አንዳንዴ የነፍስ ክፍያ ለመክፈል እንኳን የማታመነታበት ምስጢራዊ ፀጋ ነው፡፡››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ››

‹‹አሁን አንድ ምርጫ ብቻ ነው ያለን››

በንቃት‹‹ምን ?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹ሰውዬውን ፈልገን ማነጋገር››

‹‹የትኛውን ሰውዬ?››

ፈራ ተባ እያለች ‹‹የእናትህን ጓደኛ…..››ስትል መለሰችት፡፡

የሚካኤል ደም ስር በንዴት ውጥርጥር አለ‹‹እሱ እኮ ጠላታችን ነው..እዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ ውስጥ የከተተን እሱ ነው…ፊት ለፊት አግኝቼ እንድገድለው ነው የምትፈልጊው፡፡››

‹‹የሆነ ፍንጭ ለማግኘት የግድ እሱን ማግኘት አለብን…የግድ አንተ ልታናግረው አይገባም…ቆይ እስኪ››  አለችና ጠረጴዛ ላይ ያስቀመጠችውን ስልክ አንስታ ከፈተች ..ምን ልታደርግ ነው ብሎ ሲጠብቅ‹‹ስሙ ማን ነበር››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹የማ?››

‹‹የሰውዬው ነዋ››

‹‹ለሚ በቀለ ››

ስሙን ሰርች ላይ ከታ መፈለግ ጀመረች፡፡

የግብርና ሚኒስቴር ዳይሬክተር ዳይሬክቶሪት ደ/ር ለሚ  በቀለ የሚል ዜና አየች፡፡

‹‹እንዴ ሰውዬው ባለስልጣን ነው እንዴ?››

ምንም አልመለሰላትም..ዜናውን ከፍታ ለማንበብ ሞከራች…ከአምስት አመት በፊት የተፃፈ ዜና ነው፡እሱን ተወችና ….ሌላ ፈለገች ..ሶስት አራቱን ከከፈተች በኃላ በአራተኛው ትኩረት ሚስብ ዜና አገኘች‹‹የግብርና ሚንስቴሬ ዳይሬክተር ዳይሬክቶሬት የሆኑት ዶ/ር ለሚ  በቀለ በጤና እክል ምክንያት መልቀቂያ በማስገባት ስልጣናቸውን ለቀዋል ››ይላል፡፡ከአራት አመት በፊት የተለቀቀ ዜና ነው፡፡

ወደፌስብክ ገባችና በስሙ ፈለገች.. ዲአክቲቬት ከሆነ አመታት አልፈዋል፡፡

‹‹ሰውዬው ጥሩ ሁኔታ ላይ አይመስለኝም….ቆይ ለእኔ ተውልኝ››

‹‹ምን ልታደርጊ አሰብሽ….?››

‹‹ያለን ምርጫ አንድ ብቻ ነው፣ቢያንስ አሁን አንድ ነገር አውቀናል..ከአራት አመት በፊት ግብርና ሚኒስቴር ይሰራ ነበር…ስለዚህ አዛ ሄድና አሁን ሚገኝበትን አድራሻ ጠይቃቸዋለው…ቢያንስ ስልኩን ይሰጡኛል፡፡››

‹‹እስቲ እናያለን››ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡

‹‹አይዞህ ምንም አትጨነቅ..ይሄንን ነገር እንፈታዋለን….የፈለገ መስዋእትነት ያስከፍል የአባትህን ምኞት እናሳካለን….ይሄ ጉዳይ ዘሚካኤልንም ወደቤተሰቦቹ እንዲመለስ ለማድረግ ያግዘን ይሆናል፡፡››

‹‹እኔ እንጇ..ዘሚካኤል እናቱን እንደፈጣሪው ነው የሚወዳት..ለእሱ እሷ እንከን አልባ መልአክ የሆነች ሴት ነች…ይሄንን ሲሰማ ዳግመኛ ይበልጥ  እንዳይሰበር ነው የምፈራው፡፡

‹‹አይዞህ ….ከመሰበር በኃላ ያለ መጠገን ነው እኛን ሞርዶ ሙሉ ሰው የሚያደርገን፡፡ደግሞ እናትህ ጥፋት ያጠፋችው  በሚስትነቷ ነው እንጂ በእናትነቷ  እስከወዲያኛው ምሉ እንደሆነች ነው፡፡››
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////

አዲስ አለም በራሷ መኪና ግን ሹፌር እየነዳላት  ከአዳማ ወደአዲስ አበባ እየተጓዘች ነው፡፡

የተቀመጠችው ከኋላ ወንበር ላይ ሲሆን ከግራዋ የራሷ ልጅ ቅዱስ ሲኖር ከግራዋ ደግሞ የፀአዳ ልጅ ምሰር ትገኛለች፡፡

አዲስአለም ወደአዲስ አበባ የምትሄደው እናቷን ለመጠየቅ ነው፡፡ይሄ ቤተሰቦቾ አዳማ ለቀው ወደ አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ  በወር ወይም በሁለት ወር አንዴ የምታርገው ነገር ስለሆነ ማንም ለምን እንዴት ብሎ የሚጠይቃት የለም፡፡ምስርን በምን ሰበብ አስፈቅዳ ከእሷ ጋር ይዛት እንደምትመጣ ግን ግራ ገብቷት ነበር፡፡ማታ ነበር ፀአዳ ጋር የደወለች፡፡

‹‹እሺ ጓደኛዬ እንዴት ነሽ?››

‹‹ሰላም ነኝ ምነው ቀን ተገናኝተን ነበር እኮ..በዚህ መሀከል ምን ትሆናለች ብለሽ አሰብሽ?››.

‹‹አንቺ ደግሞ ከአፍሽ ቀና ነገር ቢወጣ ምን አለበት?››

‹‹በይ አሁን ምን ፈልገሽ ነው ወደገደለው ግቢ….››

‹‹በእናትሽ ነገ እነማዬ ጋር አብረን እንሂድ››

‹‹ነገ ››

‹‹አዎ ነገ››

‹‹ያምሻል እንዴ…?ስንት ስራ እንዳለብኝ  ስነግርሽ ውዬ እንዴት የማልችለውን ነገር ትጠይቂኛለሽ?››

‹‹ውይ ለካ ስራ አለብሽ..ብቻዬን መሄድ እኮ ደብሮኝ ነው››

ብቻሽን መሄድ ከደበረሽ  ታዛዥ እና ጣፋጭ የሆነ ምርጥ ባል አለሽ እሱን አስከትለሽ ሂጂ››

‹‹አንቺ እየሰማሽ እኮ ነው››

‹‹ላውድ ላይ አድርሽ ነው እንዴት የምታወሪኝ… አንቺ እኮ ቅሌታም ነሽ….ለነገሩ ሚኪን በተመለከተ መጥፎ ነገር እንደማልናገር እርግጠኛ ስለሆንኩ እንደፈልገሽ››

‹‹መጥፎ ነገር እንደማትናገሪ እኔም ምስክር ነኝ … ውሸት ግን ትናገሪያለሽ..ምን አልባት እንዳልሺው ጣፋጭ ሊሆን ይችላል ታዛዣ ግን አይደለም..ልክ እንደአንቺው ስራ አለኝ አልችልም የሚል መልስ ነው የሰጠኝ››

‹‹በቃ ከልጅሽ ጋር ሒጂ››

‹‹ወይ እንደውም ተውት ከልጆቼ ጋ ሄዳለው…ምስርን ቆንጆ አድርገሽ አሳምሪያትና ወደስራ ስትሄጂ ይዘሻት ውጭ.. በዛው መጥቼ ወስዳታለው››

‹‹ምን እያልሽ ነው?››ፀአዳ እንደመበሳጨት አለች፡፡

‹‹የራስሽው ምክር እኮ ነው፡፡ልጆቹን ይዤ ሄድና ዘና እንላለን…እናንተም ካለልጆቻችሁ ይድላችሁ…እሁድ ማታ ተመልሰን እንመጣለን፡፡››

‹‹አንቺ እኮ የሆነ መዠገር ነገር ነሽ…እኔ ለራሴ ስንት ስራ አለብኝ..?ገና አሁን እሷን ሰውነቷን ሳጥብ..ፀጉሯን ሰሰራ….››

አላስጨረሰቻትም፡፡‹‹በቃ…ጥዋት ሁለት ተኩል አካባቢ ስራ ቦታሽ እመጣና ወስዳታለው..ደህና እደሪ..እወድሻለው፡፡››ብላት ስልኳን ዘጋችው፡፡እንዳለችውም ጥዋት ስትሄድ ፀአዳ ከነንጭንጯ ልጇን ምስርን አስባና አሳምራ ነበር የጠበቀቻት፡፡

‹‹ውይ ጎደኛዬ ንዴት እንደሸወድኩሽ ስታውቂ እንዴት ትናደጂ ይሆን?›› ብላ አሰበችና ብቻዋን ፈገግ አለች፡፡

ሹፌሩ ጎሮ አካባቢ የሚገኘው የቤተሰቦቾ ቤት ካደረሳት በኃላ  ሚካኤል እንዲገዛለት ያዘዘው ዕቃዎች ስለሉ ወደመርካቶ ለመሄድ ተዘጋጀ….

‹‹በቃ ነገ አስር ሰዓት አካባቢ እዚህ ድረስ ››አለችው አዲስ፡፡

‹‹እዚህ የምትንቀሳቀሺበት አይቸግርሽም?››

‹‹ችግር የለውም..የትም የመውጣት እቅድ የለኝም…ምን አልባት የምወጣም ከሆነ ራይድ እጠቀማለው››አለችና ሸኘችው፡፡

ከዛ ልጆቹን ወደቤት አስገብታ እናቷን በቅጡ እንኳን ሰላም ሳትል ነው ወደጓሮ ሄዳ ስልክ የደወለችው፡፡ከሶስት ጥሪ በኃላ ተነሳ‹‹እንዴት ነህ ዘሚካኤል?››

‹‹ሰላም ነኝ..ግን አልተሳካልኝም ብለሽ እንዳታበሳጪኝ››

‹‹አረ ተሳክቶልኛል…መጥተናል እማዬ ቤት ነው ያለነው፡፡››

‹‹በጣም ጎበዝ…..በቃ ጎሮ አካባቢ ነው ያልሺኝ፡፡››

‹‹አዎ… ትክክለኛ አድራሻውን በሚሴጅ ልክልሀለው››

‹‹በቃ..በአንድ ሰዓት ውስጥ እመጣለው››

‹‹ጥሩ ነው..እኛም ገና አሁን መድረሳችን ስለሆነ እስከዛ ከእማዬ ጋ እንጫወታለን…በል ቻው››

‹‹አዲስ በጣም አመሰግናለው…ቻው››

ስልኩ ተዘጋ ፣፣እሷ ግን ፈዛ ቀረች…ከዘሚካኤል ጋር በዚህ መጠን መቀራረብ መቻሏ የተአምር ያህል ነው….ለዘመናት ስታልመውና ስትመኘው የነበረ ነገር ነው፡፡ግን በዚህ መንገድ ይሆናል ብላ ፈፅሞ ሀሳብ አልነበራትም..እሱ የእሷን የልብ ጓደኛ አፍቅሮ እሷ ደግሞ እሱን ከሚያፈቅራት ልጅ ጋር ለማቀራረብ ስትጥር….በራሷ ድርጊት ፈገግ አለች፡፡

‹‹ምን አለበት…. ለሚያፈቅሩት ሰው የሚያፈቅረውን ነገር እዲያገኝ መርዳት ትንሽ ህመም ቢኖረውም ግን ደግሞ ደስ የሚል ስሜት አለው፡፡››አለችና ለስሜቷ ድጋፍ ለመስጠት ሞከረች…የባሏ ሚካኤል ምስል በድንገት መጥቶ አየሩን ሞላው‹‹ፍቅሬ ምን እያሰብሽ ነው…?የገዛ ወንድሜን!!!››ብሎ በሀዘን በተሰበረ ስሜት ሲወቅሳት አየች፡፡

‹‹አንተ ደግሞ ይሄ እኮ ያለፈ ታሪክ ነው….ታውቃለህ እሱን ለማግኘት ስትጥር ነበር ከአንተ ጋር የተቀራረብኩት…ከዛ እሱም ሀገር ጥሎ ጠፋ አንተም ለእኔ ምርጥና ተወዳጅ ሆንክልኝ..እናም  በሙሉ ልቤም ወድጄ አገባሁህ››

‹‹ግን ስታገቢኝ…ወደሽ ነው..ወይስ አፍቅረሺኝ?››

‹‹አይ አንተ ደግሞ ምን ቃላት ትመነዝራለህ….ለማንኛውም..የእሱ ያለፈ የአፍላ የወጣትነት ስሜት ነው..አሁን እየቀረብኩትና እየረዳሁት ያለሁት ያንተ ወንድም ስለሆነ ብቻ ነው››

‹‹እንዴ…!!ምንድነው  ጓሮ ተደብቀሽ ብቻሽን ምታወሪው?››የእናትዬው የመገረም ንግግር ነበር ከገባችበት ቅዠት መሰል ሀሳብ አባኖ ያወጣት፡፡

‹‹አይ እማዬ ..ምንም አይደል ..የሆነ ነገር እያሰብኩ ነበር››

‹‹የሆነ ነገር..ምነው ከሚካኤል ጋር ተጣላችሁ እንዴ?››

‹‹ወይ እማዬ ምንድነው የምታወሪው..?ከሚካኤል ጋር ለምንድነው የምጣለው?››

‹‹ባልና ሚስት ለምንድነው የሚጣሉት?››

‹‹እኔ እንጃ..እኔና ሚኪ ስንጣለ አይተሸን ታውቂያለሽ?››

‹‹እሱ መልካምና ታጋሽ ባል ስለሆነ ነዋ…እንጂማ እንደአንቺ መመነጫጨቅ ቢሆን… ››እናትዬው ነግግሯን ሳታገባድድ አንጠልጥላ ተወችው፡፡

‹‹እማዬ ደግሞ… የእኔ እናት ነሽ  የእሱ?››

‹‹የሁለታችሁም…ባሌ ነው ብለሽ አምጥተሸ ካስተዋወቅሺኝ ቀን ጀምሮ እኮ ልክ እንደአንቺ እሱም ልጄ ሆኗል…በዛ ላይ አሁን ወርቅ የሆነ የልጅ ልጅ ሰጥቶኛል…በይ አሁን ነይ ግቢ ቁርስ ቀርቧል…››አሏትና ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ፡፡ 

ዘሚካኤል እንዳለውም ከአንድ ሰዓት በኃላ በራፍ ላይ ደርሶ ደወለላቸው፡፡ተዘጋጅታ ስትጠብቀው ስለነበረ ወዲያውኑ ነው ልጆቹን ይዛ የወጣችው፡፡ከግዙፉ ሀመር መኪናው ወርዶ በራፍን ከፍቶ ቆሞ እየጠበቃቸው ነበር…የስድስት አመቷ ምስር እንዳየችው ደነገጠች…..መጀመሪያ የት እንደምታውቀው ነበር ግራ የገባት..ከዛ የምትወደው ዘፋኝና ተዋናይ መሆኑን ስታውቅ ስሜቷን መቆጣጠር አቅቷት እየተንደረደረች ወደ እሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ከቆመበት እጆቹን ዘርግቶ ወደእሷ ተንቀሳቀሰ…እቅፉ ውስጥ ወደቀች.. ጭምቅ አድርጎ አቀፋትና በአየር ላይ አንጠለጠላት..የምስርን ድርጊት ያየው ቅዱስ እጆቹን ከእናቱ እጅ አስለቅቆ ኩስ ኩስ እያለ ምስር እንዳደረገችው ወደዘሚካኤል ሮጠ….አዲስአለም በልጆቹ ያልተጠበቀ ድርጊት  በድንጋጤ አፏን ከፈተች ….ሚካኤል ቅዱስ ስሩ ሲደርስ ምስርን ወደአንዱ እጁ አዘዋወራትና ጎንበስ ብሎ ቅዱስን አቅፎ ወደላይ አነሳውና ጉንጮቹን እያገላበጠ ሳመው…..በዚህ ጊዜ አዲስ አለም ከመደነቅ ሳትወጣ ስራቸው ደርሳ ነበር፡፡

‹‹ቆይ ከእነዚህ ልጆች ጋር ከዚህ በፊት ትተዋወቁ ነበር እንዴ?››

ጉንጮቾን እያገላበጠ ሰማት..ትንፋሹ ልክ ሰው ፊት ላይ እደሚበትን አደንዛዥ ዕፅ ኃይል አለው…
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነው፤ የሆነ የሚንጠጣረር ነገር እያደነቆረው ነው፡፡በመከራ ነው ከእንቅልፉ የነቃው…የበራፉ መጥሪያ ድምፅ መሆኑ አወቀ..ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ይላል፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡በዚህ ሰዓት ማን ነው በራፍን መጥሪያ የሚያንጣርረው?፡፡የፅዳት ሰራተኛዋ እንደማትሆን እርግጠኛ ነው፡፡እሷ አንደኛ በዚህ ሰዓት አትመጣም…ብትመጣም የራሷ የሆነ ቁልፍ ስላላት እሱን የምትቀሰቅስበት ምንም  አይነት ምክንያት የላትም….መኝታውን ለቆ ተነሳና ጋዎኑን ደርቦ መኝታ ቤቱን ለቆ ወጣ፡፡፡ሳሎን ደርሶ በራፉን ሲከፍት..እየተመለከተ ያለው  ፈፅሞ በአእምሮው ያልጠበቀውን ነው፡፡ፊቱን በጥፊ ደረቱን በጡጫ እየቀጠቀጠች ገፍትራ ወደውስጥ አስገብታ ትቦጫጭረው ጀመር….‹‹ምን አድርጌሀለው..?እንዴት በልጄ ስሜት እንደዛ ትጫወታለህ..?ምን አይነት አረመኔ ሰው ብትሆን ነው?፡፡››
እንደዚህ አውሬ የሆነች ሴት በእድሜ ዘመኑ አጋጥሞት  አያውቅም፡፡ፊቱን ከብጭሪያ ለመከላከል ሁለቱን  እጆቹን በፊቱ ዙሪያ አድርጎ ለመከላከል ሞከረ፡፡
‹‹አረ ፀዲ ተረጋጊ….››
‹‹አልረጋጋም..እንዲህ አሳብደሀኝ እንዴት ነው የምረጋጋው…..?ልጄን እንዴት እንዳሳደኩዋት ታውቃለህ…?››መደባደቧን እና ጮኸቷን አላቆረጠችም….እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኖ እየረገፈ ነው፡፡ትናንት የሆነውን ከሰማችበት ደቂቃ ጀመሮ ማልቀሷን አላቆረጠችም… ለሊቱን እንቅልፍ ባይኗ ሳይዞር ስትቃጠልና ስትነፈርቅ ስላደረች የእናቱን ሞት አዲስ እንደተረዳ ሀዘንተኛ አይኖቾ ከማበጣቸውም በላይ ክፍኛ ደፍርሰዋል፡፡
ዘሚካኤል መከላከሉ ብቻ እንደማያዋጣ ገባው፡፡እንደምንም አለና ሁለት እጆቾን ያዘና ስቦ ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፡፡
‹‹ልቀቀኝ..ከዚህ ቀፋፊ ሰውነትህ ጋር መነካካት …..››አላስጨረሳትም የተከፈተ አፏን በአፉ ከደነው….በተቻላት መጠን ተወራጨች…ከእሱ ፈርጣማና የዳበረ ጡንቻ ማምለጥ አልቻችም…ከንፈሩን ነከሰችው….ለቀቃትና..ተስፈንጥራ ወደኃላ ልታመልጥ ስትል መልሶ በመያዝ ሙሉ በሙሉ ከስር ገብቷ ተሸከማት……እንደእፃን ልጅ በእግሯም በእጇም ተወራጨች… ወደሶፋው ይዟት ሄደ…ሶፋው ላይ ሊወረውረኝ ነው ብላ ስትጠብቅ እሷን አጥብቆ እንደያዘ እግሩን ዘረጋና ከሳፋው ላይ አንዱን ትራስ ወደወለሉ አወረደ….በፍጥነት ገለበጣትና እንደህፃን አቅፎ ወደታች በጉልበቱ ተንበረከከ እና ወለሉ ላይ አስተኛት…ሾልካ ከስሩ ለማምለጥ ታገለች… በጥንካሬ ጨምቆ ከወለሉ ላይ አጣበቃትና ጭንቅላቱን ቀና አድርጎ ትራሱ ላይ አስደገፋት …እንዳይጨፈልቃት በመጠንቀቅ እላዩዋ ላይ  ተቀመጠ…የለበሰውን ጋወን አውልቆ ወረወረው….
‹‹ምን ልታደርግ ነው?››አይኗቾ በድንጋጤ ፈጠጡ፡፡
ወደታች ጎንበስ አለና የለበሰችውን ቲሸርት ከግራና ከቀኝ ይዞ ወደታች ተረተረው….የመጨረሻውን ንዴት በመናደዷ ምክንያት ደምስሯ ተግተረተረ‹‹ምን እያደረክ ነው? ልትደፍረኝ ነው እንዴ..?እከስሀለው…ስምህን ነው ያማጠፋው….››የቀራት ብቸኛ መከላከያ ምላሷ ብቻ ነበር….ልታስፈራራው ሞከረች ፡፡ተንጠራራና ሌላ ትራስ አምጥቶ ከጎኗ በማድረግ ከላዬ ላይ ወርዶ ከጓና ተኝቶ ወደራሱ ገለበጣትና አቀፋት፡፡
ከታች እሱ በቁምጣ ሲሆን እሷ ደግሞ ልክ እንደወትሮዋ ጅንስ ሱሪ እንደለበሰች ነው፡፡
‹‹በፈጠሪ ስትበሳጪ እንዴት ነው የምታምሪው?፡፡››
‹‹እያሾፍክብኝ ነው?››
‹‹በፍፅም ..አይገባሽም እንዴ ..?ካንቺ ፍቅር ይዞኛል…ላገባሽ እፈልጋለው››
ምትሰማውን ቃል ማመን አቃታት‹‹ይሄ ደግሞ ሌላ ቀልድ መሆኑ ነው?ሕይወት እንደምትተውነው ተውኔት መሰለህ?››
‹‹እሱ እንዳያያዝሽ ነው …እኔ ግን የተናገርኩት ከልቤ ነው…ከፈለግሽ ዛሬውኑ ሄደን መጋባት እንችላለን…እንደማገባሽ እግጠኛ ስለሆንኩ ነው ምስርን ልጄ ነች ያልኩት፡፡››
‹‹እንዴት እሺ ትለኛልች ብለህ አሳብክ?››
‹‹እንደምትወጂኝ አይኖችሽ ውስጥ ስላነበብኩ››
የተፋቀረ ሁሉ ይጋባል ያለህ ማን ነው….ደግሞ እወቅ እኔ ፍቅር አልፈልግም…አሁን ልቀቀኝ ..ከአንተ እስከወዲያኛው መሸሽና መራቅ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹አይ ከአኔ ሸሽተሸ ማምለጥ  አትችይም፡፡››
‹‹ልቀቀኝ አልኩ..›› ለመመናጨቅ ሞከረች አጥብቆ ያዛትና ከንፈሯ ላይ በድጋሚ ተጣበቀ… ሳላሳ ሰከንድ ያህል ብቻ ነው መታገል የቻለችው..ከዛ ቀስ በቀስ እየለዘበች…  የእጆቾ ጡንቻዎች እየለሰለሱ ..ከንፈሯቾ ለከንፈሮቹ መልስ እየሰጡ መጡ…እሱን ሲቧጭሩ እና ሲደበድብት የነበሩት ጣቶቹ ጀርባውናና መላ ሰውነቱን ማሻሸት ጀመሩ…ከዛ እሱ ቁምጣውን ሲያወልቅ እሷም በገዛ እጇቾ ጅንስ ሱሪዋን እያወለቀች ነበር….እዛ ግዙፍ የሳሎን ወለል ላይ 30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በፍቅር እየተንከባለሉ እና ከኮርነር  ኮርነር እየተሸከረከሩ በጣር የታጅበው ወሲብ ሲሰሩ በራፉ ክፍት መሆኑን እንኳን አላስተዋሉም ነበር፡፡
ከወሲብ በኃላ አርቃኗን ሆና ‹‹አንተ ምን አይነት አዚም ነው ያለህ ግን?››ስትል ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው የፍቅር አዚም ነዋ››
‹‹አይ አይመስለኝም…..የሆነ  የሚያደነዝዝ አይነት መስተፋቅርማ አለህ…አሁን ሻወር ቤቱን አሳየኝ..››አለችው፡፡
ከተዘረረበት ወለል እየተነሳ ወደእሷ ሄዶ ከስር ተሸክሞ ወደምኝታ ክፍሉ ተሸክሟት ገባ….‹‹ያው ግቢና ታጠቢ››
‹‹እሺ…ቲሸርቴን ቀዳደሀዋል….አሁን ምን ልለብስ ነው?››እያለች ገባች፡፡
‹‹አታስቢ አዘጋጅልሻለው….ግን አብሬሽ ሻወር መውሰድ እፈልጋለው፡፡››
‹‹ስርአት ይዘህ የምትታጠብ ከሆነ ትችላለህ›› አለችው፡፡በደስታ እርቃኑን ገባና ተቀላቀላት…መታጠብ ጀመሩ፡፡ ቃል እንደገባው ግን ስርዓት ይዞ አልታጠበም..እሷም በቃላት አውጥታ አትናገር እንጂ ስርዓት የለሽ መሆኑን ፈልጋው ነበር..ከዛ ሻወር ቤት ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነበር የወሰደባቸው፡፡ ከዛ ተያይዘው ሲወጡ ሁለቱም ሰውነታቸውን ማዘዝ እስኪያቅታቸው ዝለው ነበር.. ርቃናቸውን ተያይዘው አልጋ ውስጥ ነው የገቡት…ሁለት ሰው መሆናቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተቃቅፈው ለሞት የተቃረበ እንቅልፍ ውስጥ ገቡ፡፡
///
ተመሳሳይ የበራፍ ተደጋግሞ መንጫረር ነበር ከእንቅልፉ ያባነነው..‹‹ዛሬ ደግሞ ምን ጉድ ነው ?››በማለት እየተነጫነጨ…እንደምንም ነቅቶ ስልኩን ሲመለከት..ከ30 በላይ ሚስኮል ነበረው…ሰዓቱን ሲመለከት 7ሰዓት ተኩል ሆኗል…ማመን አልቻለም፡፡ይሄ ሁሉ ሚስኮል ከማን ነው ብሎ ሲያየው አብዛኛው ከአዲስአለም ነው…ስለፀደይ ተጨንቃ እንደሆነ ገመተ ..አልጋውን ለቆ ሲወርድ ፀደይ እራሷን አታውቅም፡፡
ጋወኑን ቅድም ሳሎን ወለል ላይ ትቶት ስለነበረ….ቁምጣ እና ቲሸርት ለበሰና በድኑን እየጎተተ ወደ ሳሎን ሄዶ በራፉን ሲከፍት ክፍኛ የደነገጠችውና አይኗ  የፈጠጠው አዲስአለም በራፉ ላይ ተገትራለች
‹‹እዚህ አልመጣችም…?ወይኔ ጓደኛዬ….›
‹‹አረ ተረጋጊ..ግቢ ››
ወደውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘግቶ ተመለሰ‹‹እሺ የት ሄደች ይባላል ?አንተ ደግሞ ለምንድነው ስልክህን የማታነሳው?››
‹‹አሁን ተረጋጊና ከተቻለሽ ቆንጆ ምሳ ስሪልን››
‹‹ምን እያወራህ ነው?ፀደይ ጠፍታለች እኮ ነው የምልህ››
#አላገባህም


#ክፍል_ሀያ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///

ዘሚካኤል እንግዳው ላይ አፍጥጦ

‹‹አይ ምንም እየገባኝ አይደለም….?››አለ

ሰውዬውም ዘሚካኤል‹‹ቁጭ በል አስረዳሀለው..››አለና ወደውስጥ ገብቶ ቀድሞ ተቀመጠ…

ፀደይ  ዘሚካኤልን እየጎተተች ይዛው መጣችና አስቀመጠችው…እሷም ተቀመጠችን ስልኳን አውጥታ ሪከርድ ላይ አደረገችና ሰውዬው የሚናገረውን ለመስማት ዝግጁ ሆነች፡፡

‹‹ምን ድረስ ታውቃላችሁ?››

‹‹እኔ ምንም የማውቀው ነገር የለም››ዘሚካኤል በትግስተ የለሽነት መለሰ፡፡

ፀደይ ዝም አለች‹‹ጥሩ ከመጀመሪያው ብጀምርላችሁ ችግር የለውም..እኔ እና እናትህ የልጅነት ጓደኛሞች ማለት ፍቅረኛሞች ነበርን…በጣም ነበር የምንዋደደው…..ምንጊዜም ስለመጋባትና ዕድሜ ዘመናችንን ሙሉ አብሮ ስለመኖር ነበር የምናስበው…ከዛ ድንገት አባቴ ወደአሜሪካ መሄድ አለብህ አለኝ…ብዙ ወንድሞቹ እዛ ስላሉ ሀሳቡን ላስቀይረው አልቻልኩም….አባቴን በጣም ነበር የምፈራው..ከዛ ጥያቄውን ተቀብዬ ወደአሜሪካ ሄድኩ…ለካ እሷ በወቅቱ እህትህን ፀንሳ ነበር..፡፡››

‹‹ፀንሳ ማለት …ከማን?››

‹‹ከማን ይሆናል ከእኔ ነዋ››

‹‹እና እህቴ የአንተ ልጅ ነች…?.ምንድነው የምትቀባጥረው?››

‹‹አልቀባጠርኩም..ከፈለክ አባትህን ጠይቀው …ያውቃል…እናትህ እኔ ጥያት ስለሄድኩ በጣም ተበሳጭታብኝ ስለነበር እና በዛ ላይ አርግዛ ስለነበር…ወዲያው አባትህን አገባችው…ስታገባው..ለልጇ አባት ለማግኘት አንጂ አፍቅራው አልነበረም…እሱም ይወዳት ስለነበረ ተንከባከባት….እህትህም በሰባት ወር እንደተወለደች ነበር ያሰበው…የገዛ ልጁ ነበር የምትመስለው….ስለዚህ ትርሲትን  እንደልጁ አሳደጋት..ከዛ አንተ እና ወንድምህ ተወለዳችሁ፡፡እኔም ከሀያ አመት ቆይታ በኃላ ከአሜሪካ ተመለስኩ፡፡ለእሷ የነበረኝ ፍቅር ከውስጤ ስላልበረደ ፈልጌ አገኘኋት…በጣም ተበሳጭታብኝ የነበረ ቢሆንም ታፈቅረኝ ስለነበረ በሂደት ይቅር አለቺኝ…አባትህን  ፈታ እኔን እንድተገባኝ እጨቀጭቃት ጀመር…እሷም ምንም እንኳን ከእኔ ጋር ለመጋባት በጣም ፍላጎት ቢኖራትም እናንተን መበተን ስላልፈለገች በሀሳቤ ልትስማማ አልቻለችም፡፡

እኔም እሷን ትቼ ሌላ ሴት ማግባት ብሞክርም አልቻልኩም..አቃተኝ…ከዛ በቃ አንቺ እሺ ብለሽ ባልሽን ፈተሸ ማታገቢኝ ከሆነ ቢያንስ ልጄን የማግኘት መብት አለኝ..ለልጄ አባቷ እኔ እንደሆንኩ ንገሪያት እያልኩ በዚህ መጨቃጨቅ ጀመርን፡፡እሷም ያንን ማድረግ አልችልም እያለች መከላከል ጀመረች፡፡በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን በድብቅ እየተገናኘን ፍቅራችንን እንወጣ ነበር…

‹‹ለምን ያህል ጊዜ ከአባቴ እየተደበቃችሁ ..እንደዛ አደረጋችሁ?››ግሽግሽ ባለና ጥላቻ በተጫነው ስሜት ጠየቀው፡፡

‹‹አራት ወይም አምስት አመት››መለሰለት

‹‹እና አባቴ ይሄን ሁሉ ታሪክ ሲያውቅ ነዋ ..ቀልቡን ነስቶት ያንን  ወንጀል የፈፀመው?››

‹‹አይ አይደለም…ስለዚህ ጉዳይ ሳስብ እስከዛሬ ድረስ ራሴን መቆጣጠር እስኪያቅተኝ  አዝናለው..እመነኝ በጉዳዩ በጣም መፀፀት ብቻ ሳይሆን ብዙ ነገሬን አጥቼበታለው….፡፡ ስራዬን፤ ጤናዬን …ብዙ ብዙ ነገር…ብዙ ጊዜም ራሴን አጥፍቼ ከልጄ ትርሲት እና ከእናትህ ጎን ለመተኛት ሞክሬ ነበር..ግን በሆነ መንገድ እተርፋለው…መጨረሻ ይሄው እንደምታየኝ የአያቴ መንደር መጥቼ በዚህ አይነት ሁኔታ መኖር ጀመርኩ..ትንሽም ወደእዚህ ከመጣሁ ነው ጤነኛ የሆንኩት››

‹‹ሰውዬ እኔ ያንተን ፀፀት ለመስማተ  ምንም አይነት ፍላጎት የለኝም..ስለዋናው ጉዳይ ንገረኝ››

‹‹ትዝ ይለኛል ቀኑ እሁድ ነበር….በእለቱ አባትህ ሞጆ የጓደኛው ለቅሶ ስለነበረ መሄዱን እናትህ ስትነግረኝ..መኪናዬን ከአዲስአበባ አስነስቼ አዳማ ሄድኩ ፡፡እናትህን ተቀጣጥረን ስለነበር ቡቲክ አገኘኋት …እሁድ በዛ ላይ ጥዋት  ስለሆነ የገበያ ግር ግር አልነበረም.. ከዛ የተወሰነ ከቆየን በኃላ የተለመደ ጭቅጭቃችንን ጀመርን‹‹ …ለልጄ አባቷ መሆኔን ወይ ቀድመሽ ንገሪያት ወይ እነግራታለው››አልኳት፡፡

‹‹እሷ ቅጣውን በልዩ ሁኔታ ነው የምትወደው …አባትሽ ቅጣው አይደለም ብላት ልጄ በጣም ነው ምትጎዳው››አለቺኝ፡፡

‹‹ብትጎዳም ለጊዜው ነው…ከውሸት ጋር ለዘላለም ከምትኖር እውነቱን አውቃ ለትንሽ ጊዜ ብትጎዳ ይሻልል››አልኳት
በዚህ ጉዳይ ላይ ለ30 ደቂቃ ለበለጠ ጊዜ በከረረ ሁኔታ ስንከራከር ቆየን….ከዛ የስልክ ንግግር ድምፅ ነው  ሁለታችንንም ያነቃን….

እህትህ ትርሲት ከባንኮኒው ማዶ … ፊቷ በእንባ ታጥቦ…አይኖቾ ፈጠውና  አውሬ መስላ ቆማለች..ሱቁ ውስጥ ገብታ እዛ የቆመችበት ቦታ መች እንደቆመች አናውቅም..ምን ያህሉን እንደሳማችንም አናውቅም….ከሁኔታዋ እንደሚታው ግን የሚበቃትን ያህል እንደሰማችን ያስታውቃል…ሁለታችንም በርግገን ጎን ለጎን ተጣብቀን ከተቀመጥንበት ተነሳን….

‹‹ለማን እየደወለች ነው?››ሁለታችንም ግራ ተጋባን፡፡ወዲያው ስልኩ ተነሳላትና ማውራት ጀመረች፡፡

‹‹አባዬ  ….ያንተ ልጅ አይደለሁም እንዴ…?እማዬና ውሽማዋ ሲያወሩ ሰማው…አባዬ እኔ ያንተ ልጅ ካልሆንኩ መኖር አልፈልግም…የሌላ ሰው ልጅ መሆን በጣም ነው የሚቀፈኝ…አይ አልጠብቅህም ..በጣም ነው የምወድህ….››አለችና ስልኩን ግድግዳው ላይ ወርውራ ከሱቁ ወጥታ ተፈተለከች፡፡ልንደረስባት ሞከርን ግን ወዲያው ተሰወረችብን፡፡

‹‹ወይኔ ልጄ….ወይኔ ልጄ…››እናትዬው ተርበተበተች....እኔም የምይዝው የምጨብጠው ግራ ገባኝ….ሱቁን ዘጋንና….

‹‹ወደየት ነው የሄደችው?››ስል እናትህን ጠየቅኳት፡፡‹‹እኔ ምናውቃለው..ወደቤት ከሄደች…ሄጄ ልያት››አለችኝ

‹‹በቃ ነይ መኪና ውስጥ ግቢ››ስላት

‹‹እንዴ ..አንድ ላይ ስንሄድ..?››

‹‹አሁን እኮ ነገሮች ተደበላልቀዋል…ምንፈራው ሳይሆን የምንጋፈጠው ነው››አልኳትና እየጎተትኩ መኪናዬ ውስጥ ይዣት ገባው፡፡በየመንገዱ እየፈለግናት…ልትሄድ ትችልበታለች ብላ እናቷ የጠረጠረችበት  አንድ ሁለት ቦታ አቁመን አይተን መጨረሻ ወደቤት ሄድን…መኪናውን ራቅ አድርጌ እንዳቆም አደረገችኝና…‹‹እኔ ገብቼ ልያትና ካለች እነግርሀለው..ከሌለችም ሌላ ቦታ ሄደን እንፈልጋታለን›› ብላኝ ገባች፡፡እኔም በጭንቀት እየተንቆራጠጥኩ መጠበቅ ጀመርኩ…5 ደቂቃ ..10 ደቂቃ አለፈ..ስልኬን አውጥቼ ስደውል እናትህ ሞባይል አይነሳም…ራሴን መቆጣጠር አቃተኝና የሆነው ይሁን ብዬ ወደግቢው ገባው፡፡ሳሎኑ በራፍ እንደተከፈተ ነበር…ስገባ  ልጄ ኮርኒሱ ላይ ተንጠልጥላለች..እናትህ ደግሞ የገዛ ሆዷን ላይ ቢላዋ ሽጣ ተዘርራለች፡፡ይመስለኛል እናትህ ወደቤት ስትገባ እህትህ ተሰቅላ እራሷ አጥፍታ ስታያት ወዲያው አካባቢው ላይ ያገኘችውን ቢላዋ ሆዷ ውሰጥ የሻጠችው ይመስለኛል፡፡

ከዛ ደንዝዤ የምሆነው ጠፋኝ…ምን ላድርግ ..?ልጄን ከተሰቀለችበት ለማውረድ ገመድ መቁረጫ ለመፈለግ ወደውስጥ ገብቼ መቁረጫ ይዤ ስመለስ አባትህ ከውጭ ከሳሎኑ ሲገባ አየሁት፡፡በደመነፍስ ወደ ጎሮ በራፍ ሄድኩ…ዞሬ ከግቢው ወጣሁና መኪናዬ ውስጥ ገብቼ ደም እንባ እያለቀስኩ ሁኔታዎችን መከታተል ጀምርኩ፡፡ ከዛ አንተና ወንድምህ አንድ አይነት ሰማያዊ የስፖርት ልብስ ለብሳችሁ ወደቤት ስትገቡ ተመለከትኩ፡፡ ከደቂቃዎች በኃላ ፖሊሶች ሰፈሩን ወረሩት…እናንተንም አባታችሁንም ፖሊሶች ይዘዋችሁ ሲሄድ የእናትህንና የእህትህን አስከሬን በአንብላንስ ሲወሰድ ከመንገድ ማዶ መኪናዬ ውስጥ ተቀምጬ እየተመለከትኩ ነበር፡፡ ሁለቱም እራሷቸውን  እንዳጠፉ እርግጠኛ ነኝ፡፡
#አላገባህም


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

/////
ዘሚካኤል ስቲዲዬ ቆይቶ ገና ወደቤት እንደገባ ነበር ስልኩ የጠራው፡፡

የደወለችለት አዲስ አለም ነበረች፡፡የጠበቀው ሚካኤል ይደውልልኛል ብሎ ነበር ፡፡ከአባቱ ጋር የሚገናኙበትን ቀን ከወህኒ ቤቱ አስተዳዳሪ ጋር ተነጋግሮ እንደሚደውልለት ነገሮት ነበር፡፡እና ይሄን ቀን በፍርሀትና በጉጉት ነበር እየጠበቀ ያለው፡፡ስለአባቱ ዜና ለመስማት፡፡ስልኩን አነሳው፡፡

‹‹ሄሎ አዲስ እንዴት ነሽ?››

‹‹ሰላም ነኝ አንተስ?››

‹‹እኔ በጣም ደህና ነኝ…ሚካኤል ይደውልልኛል ብዬ እየጠበቅኩ ነበር፡፡››

‹‹ይደውልልሀል..አሁን ኩማንደሩ ቀጥሮት ሊያገኘው ሄዶል …ከእሱ እንደጨረሰ እርግጠኛ ነኝ ይደውልልሀል፡፡…አታስብ ኩማንደሩ ደግሞ ያንተ አድናቂ ስለሆነ ከአባታችሁ እንድትገናኙ ሁኔታውን ያመቻቻል….በዛ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው

‹‹ጥሩ ታዲያ አንቺ ሰላም ነሽ?››

‹‹በጣም ሰላም ነኝ…ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ  ነበር››

‹‹ምን?››

‹‹ከፀዲ ጋር እንዴት ናችሁ?››

ያልጠበቀውን ጥያቄ ነው የጠየቀችው‹‹በጣም አሪፍ ነን…ከቦንጋ ከተመለስን በኋላ በአካል ባንገናኝም በስልክ ግን በቀን ሁለት ሶስት ጊዜ እንደዋወላለን…እንደውም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ከከተማ ወጣ ብለን ለማሳለፍ ተነጋግረናል፡፡

ግን ምነው ጠየቅሺኝ?››

‹‹ግልፅ ሆነህ ንገረኝ…ስለእሷ ምን ታስባለህ..ማለቴ አሁንም በፊት እንደነገርከኝ ታፈቅራታለህ?››

‹‹እንዴ!እንዴት በአንድ ወር ፍቅሩ ይተናል ብለሽ አሰብሽ? እንደውም ጥሩ ነገር አነሳሽልኝ…የሆነ ቀን አመቻችቼ ካንቺ ጋር መነጋገር እፈልግ ነበር..እኔ ላገባት እፍልጋለው..በቅርብ ቀን..እና እንዴት ጠይቄ ላሳምናት የሚለውን ከእኔ ይልቅ አንቺ ስለምታውቂ እንድታማክሪኝ እፈልጋለው፡፡››

‹‹እንግዲያው እንደዛ ከሆነ ሳይረፍድብህ ፍጠን››

‹‹አልገባኝም?››

‹‹ያንተን ልጅ አርግዛለች..››

የሰማውን ነገር ማመን አልቻለም…በደስታ ጮኸ…

‹‹ማለት…በፈጣሪ እየዋሸሺኝ አይደለም አይደል? ››

‹‹አርግዛለች..ለእኔም አልነገረችኝም ፡፡

በአጋጣሚ አንድ የግል ሆስፒታል  ካርድ ክፍል የምትሰራ ወዳጅ ነበረችኝ …አሁን ከደቂቃዎች በፊት ደውላ  ጓደኛሽ ፀንሳ እኛ ሆስፒታል  ለማስወረድ መጥታ ነበር…ብላ ነገረችኝ፡፡መጀመሪያ አላመንኩም ነበር..በኋላ ግን ሆስፒታሉ ድረስ ሄጄ በሌላ መንገድ እራሷ መሆኗን አረጋግጬያለው…ልታስወርደው ለተነገወዲያ ቀጠሮ አሲይዛለች….ቀጥታ ላናግራት ፍልጌ ነበር….ጭራሽ እልክ ትጋባለች ብዬ ስለፈራሁ ምንም ልላት አልቻልኩም…አንተ ምታደርገው ነገር ካለ ሞክር››

‹‹ወይኔ በፈጣሪ..ለእኔ አረገዘችልኝ…..››በበቃ ቻው አዲስ አንቺ አትጨነቂ እኔ አስተካክለዋለው፡፡

የአዲስን ስልክ ከዘጋ በኃላ ቀጥታ ልብሶቹ በሻንጣ  መክተት ነው የጀመረው፡፡ሁለት ሻንጣ ልብስና በወሳኝ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ሰበሰበና አፓርታማውን ለቆ ወጣ …ቀጥታ ወደአዳማ ነው የነዳው፡፡

ፀአዳ ቤት ሲደርስ በራፏ ዝግ ነበር..ሊደውልላት አልፈለገም ፡፡ሻንጣውን አወረደና በራፏ በረንዳ ላይ አድርጎ እሱ መኪናው ውስጥ ሆኖ መጠበቅ ጀመረ…ከምሽቱ አንድ ሰአት ስትመጣ እሱ መኪና ውስጥ ሻንጣው በረንዳ ላይ ሆኖ ስታየው ፍፁም ነው ግራ የተጋባችው…ምስር  እሱ መሆኑን ስታውቅ ከእናቷ ተነጥላ ወደእሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ፈጥኖ ከመኪናው ወረደና እጇቹን እንደክንፍ ዘርግቶ ጠበቃት…ተጠምጥማበት በደስታ ጉንጩን ትስመው ጀመር…
ወደቤት እንደገቡ ፀደይ‹‹ምንድነው ጉዱ?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹ምንም ..ለጥቂት ሳምንታት እረፍት ስለሆንኩ እዚህ ከእናንተ ጋር ለመቆየት ወስኜ ነው፡፡››

‹‹እዚህ ከእኛ ጋር?››

‹‹አዎ ከእናንተ ጋር››
ህፃኖ ምስር ‹‹ታድለን…ታድለን›› እያለች መጨፈር ጀመረች፡፡

ፀአዳ ልጇ ምስር ፊት ምንም ማለት አልቻለችም.‹‹እንግዲያው እደቤትህ ዘና በል…እኔ ልብስ ልቀይር ››አለችና መኝታ ቤት ገባች፡፡ከዛ እራት ሰርታ በሉና ከሶስት ሰዓት በኃላ ምስርን አስተኝተው ነበር እንደአዲስ ጭቅጭቁን የጀመሩት፡፡

‹‹ምን እየሰራህ ነው?››

‹‹እንደምታገቢኝ ቃል ገብተሸ ቀለበት እስክታስሪልኝ ድረስ ከዚህ ቤት ወጥቼ ወደቤቴ አልመለስም››ሲል ቁርጡን ፍርጥም ብሎ ነገራት፡

‹‹ጭራሽ ማግባት? እየቀለድክ ነው፡፡››

‹‹በፍፅም …ብቀልድ ነው እንደዚህ አይነት እርምጃ የወሰድኩት፡፡››

‹‹ስማ..እኔ ካንተ ጋብቻ ፍቅር ምናምን አልፈልግም››

‹‹ታዲያ ምንድንው ምትፈልጊው?››

ትኩር ብላ አየችው….
‹‹ንገሪኝ ከእኔ ምንድነው የምትፈልጊው….. ?››

‹‹ካንተ ወሲብ ብቻ ይበቃኛል….ማለቴ እስከአሁን የደረግነውን ለማለት ነው …ደግሞ  አሁንም እናድረግ እያልኩህ አይደለም፡፡››

በንግግሯ ሆድን እስኪያመው ሳቀ…በመሀል ስልክ ተደወለለት ..ከወንድሙ ነበር…በጉጉት አነሳው‹‹እሺ ሚካኤል ደህና አመሸህ?››

‹‹ሰላም ነኝ…ነገ ጥዋት ሶስት ሰዓት ላይ አዳማ መገኘት ትችላለህ?››

‹‹ምነው ?አባዬን እንድናገኝ ፈቀዱልን እንዴ?››

‹‹አዎ በጣም ደስ የሚለው ደግሞ አንድ ላይ እንድናገኘው ነው ያመቻቹልን ቅር ካላለህ አዲስንና ቅዱስንም ይዘናቸው እንሄዳለን››

‹‹አረ ቅር አይለኝም ጥሩ ሀሳብ …ግን አባዬ እኔን ለማናገር ፍቃደኛ የሚሆን ይመስልሀል?››ሰሞኑን ሲብሰለሰልበት የነበረውን ስጋቱን አንስቶ ጠየቀው፡፡

‹‹ትቀልዳለህ እንዴ…ከመሞቱ በፊት ማግኘት የሚፈልገው ብቸኛ ነገር እኮ አንተን ማናገር ነው…በደስታ  ነው የሚያነባው….እንኳን በአካል አግኝተሀው አባዬ ብለህ ስጠራው ሰምቶ ይቅርና ባለፈው ፎቶህን ሳሳየው እንዴት እያገላበጠ ሲስምና ሲያለቅስ እንደነበረ እኔ ነኝ የማውቀው…በል በዛ እርግጠኛ ሁን..ምንም አትጨናነቅ፡፡››

‹‹ምን ያስፈልገዋል…?ማለት ምን ይዤለት ልሂድ?››

‹‹የሚያስፈልገወን ነገር ሁሉ አዘጋጅተናል…አንተ ደግሞ ሚፈልገውን ነገር እንጠይቀውና በሚቀጥለው ዙር ትወስድለታለህ…ደግሞ ደስ የሚለው ከቦንጋ ያመጣችሁትን ከዶ/ሩ ጋር ያደረጋችሁትን ውይይት ለኩማንደሩ አሰምቼው በጣም ነው ያዘነው..እናም አባዬን ከሌሎች እስረኞች ጋር ተቀላቅሎ እንዲኖር ወስነዋል…››

‹‹በጣም የሚያስደስት ነገር ነው እየነገርከኝ ያለሀው..ወንድሜ በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንክ ታውቃለህ አይደል… በጣም ነው የምኮራብህ፡፡››

ሚካኤልም እንባ እየተናነቀው‹‹እኔም በጣም ነው የምኮራብህ››አለው

‹‹በቃ እሺ …...ሶስት ሰዓት ነው ያልከኝ አይደል?፡፡››

‹‹አዎ…መድረስ ትችላለህ አይደል…?››

‹‹በደንብ እንጂ ሁለት ተኩል ደርሼ ደውልልሀለው››

‹‹ጥሩ በቃ ደህና እደር››ስልኩን ዘጋ፡፡

ንግግራቸውን ሁሉ በገረሜታ ስትሰማ የነበረችው ፀደይ‹‹እርግጠኛ ነህ ግን ሁለት ተኩል ትደርሳለህ?››ስትል በፈገግታ አሾፈችበት፡፡

‹‹ትቆጪኛለሽ ብዬ ነው እንጂ እዚህ ነኝ ልለው ነበረ››

‹‹ልፋ ቢልህ ነው ….ግን ለእናንተ ደስ ብሎኛል››

‹‹ማለት?››

‹‹አንተና ወንድምህ እንዲህ እየተደዋወላችሁ በሰላም ማውራት መቻላችሁ ትልቅ ነገር ነው…አረ እንደውም ከመነጋጋርም አልፋችሁ መሞጋገስ ጀምራችኃል››

‹‹እድሜ ለአንቺ ….ባንቺ ቀናነትና ጥረት ነው ለዚህ የበቃነው….››

‹‹እኔን ማሞገሱን እንኳን ለሌላ ጊዜ አቆየው..በነገራችን ላይ የአባትህ ጉዳይ ላይ  ይግባኝ ለመጠየቅ ሚቻል ከአሆነ አንድ ጎበዝ ጠበቃ አግኝኝቼ ሁኔታውን አስረድቼው ነበር….››

‹‹በእውነት ..ታዲያ ምን አለሽ?››
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
 
ፀጋ አባቷ  እቅፍ ላይ እንዳለች   ፈገግ በማለት የራሄልን ትኩረት ለመያዝ ሞከረች፣ በዚህ ጊዜ እናቷ ጣልቃ ገብታ መናገር ጀመሩ ፡፡

‹‹ራሄል፣ ከዶክተር ኤሊያስን  ጋር እንድትተዋወቂ  እፈልጋለሁ። እሱ የፀጋ  ሐኪም ነው…ዔሊ ይህች ልጃችን ራሄል ናት።››

ዶ/ሩ በስሱ ፈገግ በማለት ‹‹ሰለአንቺ ብዙ ሰምቼያለው ..አንድ ቀን እንደምንገናኝ አምን ነበር›› በማለት እጁን ወደ እሷ ዘረጋ

ጨዋነት ያልጎደለው ፈገግታ ፈገግ አለችለት እና የዘረጋውን እጅን ጨበጠች፡፡ወላጆቿ ከእሱ ጋር አማች ለመሆን እያሴሩ እና እሱንም እያደፋፈሩት እንደሆነ ታውቃለች…ቢሆንም  የሱ ጥፋት አልነበረም።

‹‹የሞተር ሳይክሉ  ሰው ነህ አይደል?››

‹‹አዎ… ነኝ›› አላት፡፡

እጁ ሞቃታማ፣ ጣቶቹ ረዣዥም ነበሩ፣ እና ሲነካት ለረጅም ጊዜ በእንቅልፍ የመወሰድ አይነት የግንዛቤ ብልጭታ በአእምሯዋ ተንፀባረቆ ነበር….ስሜቱን አልወደደችውም። ‹‹በዛ ፍጥነት   ስታበር  ገርሞኝ ነበር››አለችው፣ትንፋሽ ወሰደችና  ‹‹ደግሞ ዶክተር መሆን እና …..››

‹‹እና  ምን?›› ከአንደበቷ ቀልቦ ጠየቃት።

‹‹ከተሸከምከው ሃላፊነት  አንፃር  ሞተር ማሽከርከር….አንድ ነገር ቢደርስብህስ?››

‹‹ለጊዜው አቅሜ የሚፈቅደው ርካሹ እና ፈጣኑ  መጓጓዣ ሞተር ነው. እና  ደግሞ አስፈላጊውን ጥንቃቄ አደርጋለሁ.››ሲል መለሰላት፡፡

ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ‹‹ሁሉም የሚያቀነቅናቸው ታዋቂ የመጨረሻ ቃላቶች ናቸው…ጥንቃቄ አደርጋለው..››አለች በንዴት፡፡

በመጠኑ ደፍረስ ባሉት አይኖቹ በትኩረት ተመለከታት…ከመተዋወቃቸው እየሰጠችው ያለው ጠንከር ያለ አስተያየት ግራ አጋብቷታል…

እናትዬው  ፀጋን  ከአቶ ቸርነት  እቅፍ  ወሰድና፡፡‹‹በሉ ወደምግብ ጠረጴዛው እንሄድ….ምሳ ዝግጁ ነው››ሲሉ አወጁ፡፡

ሁሉም ወደምግብ ጠረጴዛው ተከታትለው ሄዱ፡፡ራሄል፣ የተለመደውን ቦታዋ ላይ ተቀምጣለች፣ ዔሊያስ ከእሷ ፊት ለፊት ተቀምጠ።››
አቶ ቸርነት በቀኝ  እጇቸው  የሴት  ልጇቸውን እጅ ግራ እጇቸው ደግሞ  በዔሊያስ ትከሻ  ላይ ዘረጉና። ‹‹ብዙውን ጊዜ ከምግብ በፊት እንፀልያለን››ሲሉ ለዔሊያስ ገለጹለት።

‹‹እኔ ደስተኛ ነኝ. በቤተሰቦቼ ቤትም ስርዓቱ እንዲሁ  ነው.››ሲል መለሰ፡፡አባቷ እጇን ጨምቀው ነበር፣መጸለይ ሲጀምሩ አንገቷን ዝቅ አደረገች።አባቷ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገሩ ማዳመጥ ብትጀምርም  ከጸሎቱ ጋር በልቧ መቀላቀል አልቻለችም። እሷ በሀይማኖት ስርዓት ውስጥ ተወልዳ ያደገች ቢሆንም፣ ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ ከመስመር ወጥታለች። አምላክ  በህይወቷ ጣልቃ እንዲገባ አትፈልግም ወይም  ደግሞም እሱ ራሱም ለእሷ ደንታ እንደሌለው ታምናለች።ስለዚህ ለምን ትጨቀጭቀዋለች፡፡ ወላጆቿ በዚህ መሳኔዋ  ደስተኛ እንዳልሆኑ በደንብ ታውቃለች ቢሆንም ግን ርቀታቸውን በመጠበቃቸው ታመሰግናቸዋለች። እና ምናልባት ወደቀልቧ እንድትመለስ ዘወትር ለእሷ በድብቅ ይፀልዩላት ይሆናል፡፡

ፀሎቱ ተገባዶ በ‹‹አሜን›› እንደተዘጋ እናትዬው ‹‹በሉ እራሳችሁን አስተናግዱ ››አለቻቸው፡፡ሁሉም ፊት ለፊቱ ባለው ሳህን ላይ ፊለፊታቸው ከተደረደሩት በርካታ የምግብ  ዓይነቶች የሚፈልጉትን  መጠን መውሰድ ጀመሩ፡፡ተ

‹‹ከቻልክ ክትፎውን  አቀብለኝ››ስትል ራሄል ወደኤልያስ እያየች አጉተመተመች፣
እናትዬው የራሄልን አስተያየት ውድቅ በማድረግ እጆቿን እያወዛወዘ ‹‹እስኪ እንደአንበሳ ስጋ ማሳደድሽን አቁሚ።››በማለት ገሰፃት፡፡  ቀጠል አደረጉና ‹‹ለሚያገባሽ ሰው አዝንለታለው።››ሲሉ  አከሉበት፡፡

‹‹ደህና፣ ደስ ሚለው ነገር ፍቅረኛ  የለኝም ››አለች ራሄል፡፡
‹‹እነዚህማ የተለመዱ ቃላቷችሽ ናቸው››

እናቷ በራሄል ንግግር ተከፍተው ‹‹አንድ ቀን ያንን በብቸኝነት  የቀዘቀዘ አፓርታማሽን እርግፍ አድርገሽ ጥለሽ  እንደ ዶ/ር ኤሊያስ ቤት አይነት  ግቢ  ወዳለው ቤት ትቀይሪ ይሆናል።››ሲሉ  ምኞታቸውን ተናገሩ፡፡

እናትዬው  ወደ ዶ/ሩ  ዘወር አሉን‹‹ቤትህን በማስተካከል ላይ እንዳለህ ሰምቼያለው?››

‹‹በእውነቱ ወንድሜ ቢንያም ነው እየተከታተለው ያለው። እሱ አናጺ  ነው። ስለ ኩሽና አሰራር አንዳንድ ውሳኔዎችን እንድወስን እየጨቀጨቀኝ  ነበር, ነገር ግን ዘመናዊ ይሁን ወይም ባህላዊ ጭብጥ ይኑረው  የሚለውን ለመወሰን  እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም››

አቶ ቸርነት‹‹ራሄልን  ይዘሀት ብትሄድ ልትረዳህ ትችል ይሆናል››የሚል ሀሳብ አቀረቡለት። ዔሊያስ የራሔልን መኮሳተር ችላ በማለት እንደ ተወደደ ልጅ ፊቱ እያበራ ነው።
አንቷም ‹‹አዎ የእኔ ልጅ …በኢንቴርዬር ዲዛይን  ላይ በጣም ጎበዝ ነች።››ሲሉ  የአባትዬውን ሀሳብ ደገፉ፡፡

ራሄል ስለእሷ የተሰጠ ያለው  አስተያየት ከየት እንደመጣ አታውቅም። ወላጆቿ አፓርታማዋን  በሚጎበኙበት ጊዜ  በዕቃዎቾ፤በምንጣፎች እና በመኝታ ቤቷ ቀለም ..ብዙ ብዙ ኔጌቲቨ  የሆነ አስተያየት ሲሰጧት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡ እንደውም እናቷ ‹ጥቂት እንኳን ለስሜቷ ሳይጨነቁ ቤቷን መኖሪያ ቤት ሳይሆን ሙዚየም እንዳስመሰለችው ነግረዋት  ነበር፡፡

‹‹የምፈልገውን በትክክል  አውቃለሁ። ትልቁ ችግሬ ግን ውሳኔዎችን ለመወሰን  ጊዜ ማግኘት አለመቻሌ ነው ›› ሲል ኤሊያስ መለሰ።

ራሄል የሆነውን ነገር የተረዳች መስላ‹‹እንድትጨርሰው  የምትገፋፋህ  ሴት የለችም?››ስትል ጠየቀችው፡፡
አባቷ  ራሄልን በግንባራቸው ገፆት ፡፡
ዶ/ሩ ‹‹ለጊዜው አቋሜ ልክ እንደአንቺው ነው….ለሴት ዝግጁ አይደለሁም››ሲል መለሰ።
ራሄል ውይይቱ ወደ መሃል ከተማ የትራፊክ ፍሰት፣ የኑሮው ውድነትና   ፣ እና የፖለቲካ ውዥንብር.እና የሰላም እጦት  የመሳሰሉት ጉዳዬች ላይ ሲያተኩር እፎይ አለች፡፡
በመሀል ወደ ዶ/ሩ አትኩራ እየተመለከተች ‹‹በቅርቡ የኖብል ፋውንዴሽን አመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት  አለ።በዝግጅቱ ላይ መገኘትህን ማረጋገጥ አለብህ››አለችው፡፡

‹አረ ችግር የለውም..አታስቢ እገኛለው››ሲል ቃል ገባላት፡፡
እናትዬው‹‹ቀኑ ደረሰ እንዴ..?እንግዲህ በስራ ጫና ድራሽሽ ሊጠፋ ነው››ሲሉ ስጋታቸውን ገለፁላት፡፡

ራሄል  ‹‹እማዬ ደግሞ ….እኔ ብቻዬን የማደርገውን አስመሰልሺው ። አብዛኛውን ስራ የሚሰሩልኝ  ትላልቅ ሰራተኞች አሉኝ እኮ››

‹‹ነገር ግን ለሰራተኞችሽ  በቂ ውክልና አትሰጪም።ቅድስትን ለመተካት እነዚያን ሁለቱን ረዳቶች መቅጠርሽን ስሰማ  ብዙ  የስራ ጫናሽን ያቃልሉልሻል ብዬ አስቤ ነበር። ነገር ግን አሁን እንደማየው ከሆነ የበለጠ ስራ ነው ያበዛብሽ፡፡››

‹‹ሰራተኞቹ  በጣም አዲስ ናቸው ። ፋይሎቹን ብቻ ሰጥቻቸው ሁሉንም ነገር በራሳቸው እንዲቋቋሙት  መጠበቅ አልችልም።››

‹‹ዬኒቨርሲቲ ዲግሪ ያላቸውና …በደንብ የሰለጠኑ ናቸው እኮ።››

‹‹አዎ ትክክል ነሽ..ግን የፋውንዴሽኑን ስራ በተመለከተ ትንሽ ተጨማሪ ልምድ ያስፈልጋቸዋል፣ሁሉም ሰው ወደሆነ አዲስ ስራ ሲሄድ ለተወሰነ ጊዜ ከአሰራሩ ጋር እስኪለማመድ አዲስ ሆኖ መገኘት አይቀርም››ለእናቷ ሌላ የማስጠንቀቂያ እይታ ሰጠቻት። ይህን ጉዳይ ሙሉ በሙሉ በማያውቁት ሰው ፊት መወያየታቸውን አልወደደችውም ።
‹‹ውዴ እወድሻለሁ፣ ግን ደግሞ አውቅሻለሁ።››ሲሉ  እናትዬው በአቋማቸው መፅናታቸውን አረጋገጡላት፡፡

የራሄልን ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት ‹‹እና ሁሉንም ነገር መቆጣጠር እንደምትችይ  ማሰብ ማቆም አለብሽ። አንዳንድ ነገሮችን ለእግዚአብሔርን መልቀቅ አለብሽ።››ሲሉ ንግግራቸውን ደመደሙ፡፡
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

ከወ.ሮ ላምሮት ጋር የተደረገው ስብሰባ በጣም ረጅም ጊዜ ወስዶ ነበር እና  ውጤቱ በጣም ጥቂት የሚባል ነበር፡፡

ራሄል  በጣም የደክማት ቢሆንም  ቢሮዋ ገብታም ስራዋን ቀጥላለች፡፡

‹‹ጥሩ ነው…በብሮሹሮች ላይ ስህተቶችን አግኝቻለሁ.››

ሎዛ  ወረቀቶቹን በመካከላቸው ባለው የእንጨት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች። ራሄል በተቀመጠችበት የቆዳ  ሶፋ ላይ ወደ ኋላ ተደግፋ ከፊቷ ያለውን  ብሮሹር  ቃኘች። ‹‹ይህ ሰማያዊ ቀለም በጣም ደማቅ ነው….እና ይህ ቢጫው ደግሞ እንዲጠናከር እፈልጋለሁ። የቀረውን ደግሞ ደውዬ አሳውቃቸዋለሁ››

‹‹ለምን ያን እኔ ራሴ  እንድከታተል አትፈቅጂልኝም?›› አለች ሎዛ

‹‹አመሰግናለሁ ሎዛ.. ግን ማየት የምፈልገውን በትክክል አውቃለሁ።››

ሎዛ  ራሷን በይሁንታ ነቀነቀች፣  ራሄል ግን  በእሷ ውሳኔ ደስተኛ እንዳልነበረች አይታለች።

‹‹ለአሁን እንዳደርግ የምትፈልጊው ሌላ ነገር አለ?››ሎዛ ጠየቀች።

‹‹ አይ ምንም የለም… በቃ እጅሽ ላይ ያሉ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጊ።››የሚል ትእዛዝ ሰጠቻት፡፡

ራሄል ወረቀቶቹን በጠረጴዛዋ ላይ አስቀመጠች እና ሎዛ ቢሮዋን ስትለቅ ወደ ሮቤል ዞረች።

‹‹ሮቤል አንተ የሆነ ነገር አንድታደርግልኝ እፈልጋለው››አለችው፡፡

ሮቤል ጎንበስ ብሎ ከቆዳው ቦርሳ ውስጥ አንድ ወረቀት አወጣና‹‹ጥቂት ስልክ ደዋውዬ ከምንጩ  ያገኘሁት  መረጃ ነው።›› በማለት ተጨማሪ ወረቀቶችን አቀበላት።

‹‹ከስብሰባው ጥቂት ቀደም ብሎ ከድርጅቱ ኃላፊ ጋር በግል ተወያይቼ ነበር።››

‹‹ጉልበቱን ከየት አመጣው?››ስትል አሞገሰችው፡፡ ራሄል ከወ.ሮ ላምሮት  ጋር ከተገናኘ በኋላ ስላከናወናቸው ውይይቶችና ስለተለዋወጦቸው ቃላቶች በማሰብ ደክሞት  ነበር።‹‹ይህ በጣም ጥሩ ነው፣ቀጣዩ እርምጃችን የበጎ አድራጎት ልገሳ ሁኔታቸውን ማረጋገጥ እና ከቻልን በእነሱ ላይ አንዳንድ ጥልቅ የጀርባ ስራዎችን መስራት ነው።››

‹‹እንደተፈጸመ ቁጠሪው.››ሲል ሮቤል ፈገግ አለ። በዚህ ጊዜ ስልኳ ጠራ…እናቷ መስመር ላይ ነበረች።‹‹እንደገና አመሰግናለሁ ሮቤል።በቅርብ ጊዜ ፋውንዴሽኑን እንደተቀላቀለ ሰው ምርጥ ስራ ሰርተሃል.›› ብላ ስልኩን አነሳች፡፡

ራሱን ነቀነቀና ዞር ብሎ ከቢሮ ወጣ።ራሄል ከኋላው ባለው ትልቅ የቆዳ ወንበር ላይ ለመቀመጥ በጠረጴዟ ዙሪያ  ዞራ ሄደች።

‹‹ጤና ይስጥልኝ እናቴ››

‹‹ደህና ነኝ የእኔ ልጅ››

‹‹ እየሮጥኩ ያለሁት ባንቺ  ጉዳይ እንደሆነ ከግምት ውስጥ በማስገባት ልትደሰቺ ይገባሻል።››ስትል ራሄል ወንበሯ ላይ በመቀመጥ ተሸከረከረች፡፡

‹‹ውዴ፣ ሁሌም በአንቺ ደስተኛ ነኝ ፡ ታውቃያለሽ?››

‹‹እማዬ አውቃለው…የቸኮሌት ኬኩ በጣም ጥሩ ነበር. ሮቤል እና ሎዛ  አመስግኚልኝ ብለዋል.››

‹‹እንደተካፈላችሁት  በማወቄ ደስተኛ ነኝ። ግን አንቺን አንድ ውለታ ልጠይቅሽ ነው። አያቶችሽ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ወደ አድዋ ሄደን እንደንጠይቃቸው ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን  ፀጋን ይዘን ለመሄድ መድፈር አልቻልንም ።እስክንመለሰ እሷን  ለመጠበቅ ፈቃደኛ ነሸ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡ራሄል  በድንጋጤ ስልኩ ሊያመልጣት ነበር..በመከራ ነው አጥብቃ የያዘችው።

‹‹ፈቃደኛ? ምናልባት…ቆይ እስኪ ፕሮግራሜን ልመልከት››አለችና የቀጠሮ ደብተሯን ለማየት ማስታወሻ ደብተሯን ከፈተች።  በዛን ወቅት የማይሰረዝ ፕሮግራም ኖሯት ያንን እንደምክንያት ማቅረብ እንድትችል በውስጧ ፀለየች፡፡

የወሩ የመጨረሻ ቅዳሜና እሁድ…..ቢንጎ …የበጎ አድራጎት ፈንድ የመሰብሰብ ፕሮግራም አለባት። ‹‹ይቅርታ እማዬ ባልሻቸው ቀናት መሰረዝ የማልችላቸው ፕሮግራሞች አሉብኝ…በነዛ ቀናት  አመታዊ የፋውንዴሽኑ ፈንድ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አለብኝ ።››

‹‹ኦህ ውዴ፣ አያትሽ ቤት የሚውለው ቅዳሜና እሁድ ብቻ ነው።›› በለሆሳስ ተነፈሰች። እና ፀጋን  ከማንም ጋር ልተዋት እችላለው? ….እንደምታውቂው እስካሁን በጣም ደካማ ነች።››

‹‹ለምን ስለችግርሽ ከዶክተር ዔሊያስ  ጋር አታወሪበትም››ስትል ሀሳብ አቀረበች።

‹‹በእርግጥ ትክክል ብለሻል .. እሱ የግል ነርሲንግ ኤጀንሲን ወይም ተመሳሳይ ነገርን ሊመክረኝ ይችላል?››

ራሄል አሰበች፤ የጥፋተኝነት ስሜት ሊሰማት አይገባም። ወላጆቿ ይችን ልጅ ለማሳደግ መወሰናቸው  የሷ ሀሳብ አልነበረም። እና ፀጋ ብቃት እንደሌላት እና አቅመ ቢስነት እንዲሰማት ያደረጋት የሷ ስህተት አልነበረም።

‹‹እሷን መንከባከብ ካልቻልሽ ችግር የለውም…›› እናቷ ቀጠለች‹‹እርግጠኛ ነኝ ዔሊ ፀጋን የት ልንወስደት እንደምንችል ያውቃል።››

‹‹እንደሚያውቅ  እርግጠኛ ነኝ››ስትል ራሄል ተስማማች፣ እፎይታም ተሰማት።

‹እና ስለ ዶክተር ዔሊያስ ምን አሰብሽ? ››እናትዬው እንደቀልድ ሌላ ርዕስ ከፈተች፡፡

‹‹እሱ በጣም ደስ የሚል ሰው ነው…. ከፀጋ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለው ››

ከእሷ ጋር ሊጣመር የሚችልበት ምንም እድል እንደማይኖር  ለእናቷ ግልፅ ለማድረግ ጊዜው አሁን እንደሆነ ተሰማት ‹‹ግን እሱ የእኔ ምርጫ አይደለም ።››ስትል መለሰችላት፡፡

‹‹ምን አልሽ?››

‹‹እማዬ… እባክሽ አሁን ለማንም  ቢሆን ጊዜ የለኝም… ታውቂያለሽ››

‹‹ባለፉት ስምንት አመታት ውስጥ ለማንም ጊዜ አልነበራሽም። ብዙ ማህበራዊ ህይወት የለሽም። የምታደርጊው አንድ ነገር ቢኖር ስራ መስራት ብቻ ነው።››

ራሄል ወንበሯን ትንሽ እያወዛወዘች ፊቷን ከሰከሰች። ‹‹ይህን ስራ እፈልገዋለሁ እናቴ…ለህይወቴ ትርጉም የሰጠኝ ስራዬ ነው››

‹‹ከጌታ ጋር ያለሽ ግንኙነትስ? ያ እንዴት አድርጎ ነው  ስራሽን  የሚጋፋው?››ወደ ማትፈልገው ሌላ  ርዕስ ከተተቻት፡፡

‹‹‹እናቴ ሆይ፣ የእኔ ስራ የተቸገሩ ህፃናትንና  አቅመ ደካሞችን መርዳት ነው። ኢየሱስ በዚህ ምድር እንድናደርግ የሚፈልገውን ተግባር ነው እያደረኩ ያለሁት።››ራሄል እናቷን የሚያስደስት ትክክለኛ ቃላቶችን ታውቃለች እና ያለ እፍረት ተጠቀመችባቸው፡፡

‹‹ያለ እምነት ሥራ የሞተ ነው ውዴ።›› እናቷ ወደ እምነቷ ሲመጣ…ጥልቅ የማሰብ ችሎታ ስላላት  ሁሉንም የልጇን የማጭበርበሪያ ስልቶች ታውቃለች።

ራሄል በመጨረሻ ‹‹እኔ ማድረግ የምችለው  ይህን ብቻ   ነው እናቴ››አለች. ቀጠለችናም ‹‹ለወንድ ጓደኛ ጊዜ የለኝም እና ለአንድም ሰው ፍላጎት የለኝም። ስለዚህ እባካችሁ ከአሁን በኋላ የማልፈልገውን አይነት አስጨናቂ እራት ለማዘጋጀት አትሞክሩ።››ስትል ንግግሯን በመኮሳተር ደመደመች፡፡

የእናቷ ዝምታ እጅ የመስጠት ምልክት እንደሆነ ተስፋ አድርጋ ነበር።‹‹ደስተኛ ነኝ እማማ›› እናቷ ብርሃኑን እንድታይ ለማድረግ ቆርጣ ገፋችበት። ‹‹ዓላማ እና ትርጉም ያለው  ንቁ ህይወት ነው እየኖርኩ ያለሁት ። ጓደኞች አሉኝ እናም በማህበረሰብ ውስጥ  አስፈላጊ የሚባል  ስራ አለኝ። እና አንቺ እና አባዬ እና ፀጋም  አለችሁልኝ። ተጨማሪ አያስፈልገኝም።››

‹‹እሺ፣ ይቅርታ፣ አንቺና ዔሊ ትመጣጠናላችሁ ብዬ ስላሰብኩ ነው። እሱ ጥሩ እና ደግ ሰው ነው..ለዛ ነው ከእሱ መዛመድ የፈለኩት ።››

ራሄል ፊቱ ላይ ስለተመለከተችው ፈገግታ አሰበች‹ደህና፣ ለአንድ ሌላ ሴት ግሩም ባል እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ። ግን ያቺ ሴት እኔ አይደለሁም፣ እማማ።››

ወ.ሮ ትርሀስ ቃተቱ። ‹‹ካስከፋሁሽ ይቅርታ።››

‹‹አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጠርሺብኝ እንጂ አላስከፋሺኝም።››
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አራት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


እሁድ የእረፍት ቀን ስለሆነ ኤልያስ ከወንድሙና ከጓደኛው ጋር ካፌ ቁጭ ብለው ቁምነገሩንም ቀልዱንም ሲጫወቱ አረፈድና ሌላ የሚሄዱበት ቦታ ስለነበር ተያይዘው ወጡ፡፡ሶስቱም የቢኒያም መኪና ወዳቆመችበት ቦታ እየተለፉ እየሄዱ ሳለ ድንገት ኤልያስ ከወንድሙ ከቢኒያም ጉሽሚያ ለማምለጥ ወደኃላው ሲሸሽ ከአንድ ውብ ሴት ጋር ተላተመ ፡፡ሴትዬዋ በእጇ የያዘችው ወረቀቶቿ ከእጆቿ ተንሸራተው ወደቁ  እና ቦርሳዋ ከተከሻዋ  ተንሸራቶ ሊወድቅባት ነበር…እሷም ተነገዳግዳ ሚዛኗን ለመሳት ስትጥር  ኤልያስ በፍጥነት ተስፈነጠረና ክንዷን ያዛት  ። ተረጋግቶ ሲያያት አይኖቹን ማመን ነው ያቃተው ።፡ራሄል ነች፡፡ ሞባይል ስልኳ አንድ ጆሮዋ ላይ ተጣብቆል…ስልክ እያወራች እንደነበር ተገነዘበ፡፡

አቀርቅራ የተበተኑ ወረቀቷቾን እያየች‹‹ምንድነው…አይንህ አያይም እንዴ? አብደሃል?››ስትል ጮኸችበት ።ከዚያም ቀና ብሎ አያት።ሀዘን  ያረበባቸው አይኖቿ እሱን ሲያዩት ፣ ንዴቷ በጥልቀት ወደ ውስጡ ዘልቆ ሲገባ ተሰማው። በልቡ ክልል ውስጥ የሆነ ቦታ ላይ የብርሃን ብልጭታ ፈነጠቀ።ድንገት ወደጎን ዞር ብላ እሱ መሆኑን ስታውቅ በንግግሯ አፈረች፡፡‹‹እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ››ብላ አጉተመተመች፣ክንዷን ወደኋላ ጎተተች። አሁንም እንደያዛት ረስቶት ነበር። ፈጠን ብሎ  ለቀቃት። ርቀቱን ጠብቆ  በጉጉት እያዩ ወደነበሩት ወንድሙ እና ጓደኛው  እየተመለከተ። ‹‹ይቅርታ አላየሁሽም….ከወንድሜ ቢኒ ጡጫ እራሴን ለማራቅ   እየሞከርኩ ነበር.››አላት፡፡

‹‹ምንም አይደለም፣ እኔም ቀልቤ  የማወራው ስልክ ላይ ስለነበር መጠንቀቅ አልቻልኩም ።›› በማለት ወረቀቶቿን ለማንሳት ጎንበስ አለች።

‹‹ቆይ እኔ ላንሳልሽ›› ብሎ እሱም ጎንበስ አለ… ሁለቱም በአንድነት እጇቸውን ወደወረቀቱ ሲሰዱ እርስ በርስ ተነካኩ ፡፡በመሀከላቸው የኤሌክትሪክ ንዝረት አይነት ቅፅበታዊ ብልጭታ ተፈጠረ፡፡

‹‹እባክህ አትጨነቅ››  የውስጥ ስሜቱን  የሚቆሰቁስ  አይነት እንደገና የሚያነቃቃ ፈጣን ፈገግታ ሰጠችው።

ወረቀቶቹን ሰብስበው ከተነሱ በኋላ‹‹ለመሆኑ እዚህ ሰፈር ምን እግር ጣለሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹ለስራ ጉዳይ››ስትል አፏ ላይ የመጣላትን ምክንያት ሰጠችው፡፡

‹‹ በእረፍት ቀን ትሰሪያለሽ እንዴ?››

ራሄል ፊቷን አኮሳትራ‹‹ስራ እስካለኝ ድረስ ቀን ሳልመርጥ ነው የምሰራው..ታውቃለህ  …ሥራዬ በጣም አስፈላጊ ነው።››ስትል መለሰችለት፡፡

‹‹ደህና፣ በቃ እንገናኛለን።››

‹‹ተስፋ አደርጋለው።›› አለችና መንገዷን ቀጠለች ፡፡

‹‹አሁንም አለሽ ራሄል?›› ከያዘችው የሞባይል ስልክ የአንድ ወንድ ድምፅ ተሰማ። እናም ራሄል እስከአሁን ስልኳ እንዳልተቆረጠ ስትረዳ  ‹‹ ሮቤል በቃ ቆይቼ ደውልሀለው … መንገድ ላይ ያልሆነ ነገር አጋጥሞኝ ነው›› ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡

ከዛም እርምጃዋን ሳታቋርጥ  ወደ ዔሊያስ ዞር ብላ ተመለከተች …በተገተረበት ቆሞ እያያት ነበር ..የሆነ ውርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማት ፡፡መንገዱን አቋርጣ ወደካፌው ታጠፈችና ከእይታው ተሰወረች፡፡

ሁኔታውን በትኩረት ሲከታተሉ የቆዩት  ቢንያም እና ጓደኛው ወደ እሱ  ሮጠው ከጎኑ ቆመ

‹‹በቀጣዬቹ አመታት ውስጥ ያለህ የሕይወት እቅድ ውስጥ  ሴት እንደሌለችበት ደጋግመህ ነግረኸኝ ነበር? ››አለው ቢኒያም፡፡

‹‹እና ታዲያ?››

‹‹እናማ ይህቺ ሴት ማን ነች?።››

ዔሊያስ  ለወንድሙ  ‹‹የህይወት እቅዴ ላይ ምንም ማስተካከያ አልተደረገበትም..ያንን ካወቅክ ይበቃል።››ብሎት ወደመኪናው ጉዞውን ቀጠለ፡፡

ወንድሙም ከኋላው ተከትሎት‹‹እቅድህን ማስተካከል ትችላለህ …በቅድሚያ ግን ብድርህን ክፈል፣ ሞተርህን ሽጥና ትክክለኛ መኪና ግዛ፣ ከዛ  ኑሮህን የምትጋራ ሴት መፈለግ ትችላለህ››አለው

ዔሊያስ ሕይወት ሁል ጊዜ እንደማይተነበይ ከግል ተሞክሮ ያውቃል ።  ዔሊ በስድስት ዓመቱ ወደ ማደጎ ቤት ለመግባት ተገዶ ነበር፡፡   በወቅቱ ጮርቃ  ልጅ ነበር  እና ስለ ተፈጥሮ ወላጆቹ የሚያውቀው ብቸኛው ነገር አባቱ ሉቃስ እናቱ ደግሞ ትእግስት እንደምትባል ብቻ ነው፡፡ስለ እነሱ ያለው የመጨረሻ ትዝታ ቤተሰቡ በአንድ ላይ ሆነው እየተጓዙ እያለ አባቱ መኪናውን መቆጣጠር ተስኖት ሲጯጯሁ  ነበር፡፡አንድ አመት ሙሉ በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ተጣለ፡፡በዛን ተመሳሳይ ወቅት ቢኒያምም የአንድ አመት ህፃን ሆኖ በወላጇቹ ተጥሎ እዛ ማደጎ ቤት ከእሱ ጋር ነበር፣ እንደእድል ሆኖ አሳዳጊዎቻቸው ለሁለቱም ልባቸው ራራና አንድ ላይ ወደቤታቸው ወስደው እንደገዛ ልጇቻቸው ተንከባክበው አሳደጓቸው..እነሱም እርስ በርስ የሚዋደዱና የሚደጋገፉ ወንድማማቾች ሆነው አደጉ፡፡ አሳዳጊ ወላጆቻቸው ሁለቱንም በፍፁም ፍቅር እና  …በስርዓት አስተምረው ለዚህ ደረጃ አበቁዋቸው፡፡

ቀጥታ ጓደኖቾ ይጠብቋት ወደነበረው ካፌ ገባች፡፡በጠረጴዛ ዙሪያ እየተጨዋወቱ እና እየሳቁ  ካሉት ከጓደኞቿ ጋር ተቀላቀለች፡፡

‹‹ደህና ናችሁ ፣ ውድ ጓደኞቼ››

እንዴት ነሽ ንግስቲቷ›› ሜሮን ነች ቀድማ ለሰላምታዋ መልስ  የሰጠቻት፡፡ከዛ ያሬድና ሌንሳ ተከተሉ፡፡እነዚህ ሶስቱ የልጅነት የትምህርት ቤት  ጓደኞቾ ናቸው፡፡ራሄል ልጅ ሆና  ፈጣን እና ጎበዝ ተማሪ ነበረች እና በዚህ ምክንያት ሁለት ክፍል በመዝለሏ ትምህርት ቤት ከገባችባቸው ልጆች ትንሿ ነበረች።   አንድ ቀን በክፍሏ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ልጃገረዶች በመጫወቻ ስፍራው ላይ ወደ  ጥግ ወስደው  ይሳለቁባት ጀመር። እንደአጋጣሚ ሶስቱ ጓደኛሞች በአካባቢው ሲያልፉ ሁኔታውን ተመለከቱ ..ዝም ብለው ሊያልፉ አልፈለጉም…ጣልቃ ገብተው  ራሄልን በክንፋቸው ስር ከልለው ታደጓት። ከዛን በኃላ ቋሚ ጓደኞቾ ሆኑ..ይሄው እስከዛሬ በህይወት ውጣ ውረዶች ውስጥ፣ የእርሷ ምስጢረኞች አማካሪዎች እና ውድ ጓደኞቿ ሆነዋል።እና  ከአራት አመት በፊት ሌንሳና ያሬድ የጓደኝነት ግንኙነታቸውን ወደፍቅር ቀይረው በመጋባት  መንታ ልጆችን ለመውለድ ችለዋል፡፡

ያሬድ  የራሄልን የተዘበራረቀ ሸሚዞን እና የተበታተነ ወረቀቷን ተመለከተና ‹‹ደህና ነሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹አዎ..ደህና ነኝ››

‹‹ቆይ ምን ሆንሽ?››ሜሮን ተቀበለችው፡፡

‹‹ከመኪናዬ ወርጄ ወደእዚህ ስመጣ ..፣ከአንድ ጓረምሳ ዶ/ር ጋር ተጋጨው ››

‹‹ምን…!ከጎረምሳ…?ወይስ ከዶክተር?››ሌንሳ ጠየቀቻት፡፡

‹‹ጓረምሳ የሆነ ዶ/ር ..ምነው ግልፅ አይለም እንዴ?››

‹‹እኔ ያልገባኝ..ጎረምሳ መሆኑን በእይታ አወቅሽ እንበል..ዶክተር መሆኑንስ?››ሜሮን ጠየቀች፡፡

‹‹ባክሽ የማውቀው ሰው ነው …የእህቴ የፀጋ  ዶክተር ነው፡፡››ሸሚዙ እንደተከፈተ፣ እና ፀጉሩ በግንባሩ ላይ ተደፍቶ  እንደነበረ  ላለማሰብ ታገለች።

ሁሉም በአንድ ላይ አስካኩባት፡፡

‹‹ስሙ ማን ነበር?››ሌንሳ በማሾፍ ጠየቀች፡፡

ራሄል ግን ጥያቄዋን በቁም ነገር ወስዳ‹‹ዓሊ››ስትል መለሰች፡፡

‹‹ኤሊ ማለት?››ያሬድ በገረሜታ ጠየቀ፡፡

‹‹ማለቴ ኤልያስ….ዶ/ር ኤልያስ››
ሌላ የህብረት ሳቅ ተከተለ፡፡

‹‹ተመልከቷት ነገሩ ስር የሰደደ ይመስላል ። የዔሊን ስም ሲነሳ  መልኳ በደቂቃ ተለወጠ›› ሜሮን  ጮኸች።

‹‹እንዴት ነው ግን…?››ለሊሴ ጠየቀቻት፡፡

‹‹ እሱ ቆንጆ ነው ማለት ይቻላል...›› ቡድኑን ዞር ብላ ተመለከተች እና በራሷ ሳቀች።‹‹እንደ ያሬድ ወንዳ ወንድ ነው›› ስትል አከለችበት፡፡
ሁሉም ሳቃቸውን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_ስምንት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ



ራሄልም እህቷን ይዛ እቤት እንደገባች ጓደኛዋ  ሜሮን ቤት እየጠበቀቻት ነው፡፡መጀመሪያ ቀጠሮውን ለመሰረዝ ፈልጋ ነበር…በኋላ ስታስበው ግን ሴትዬዋ ለስብሰባው ትኩረት እንዳልሰጠች አድርጋ ልትረዳት እንደምትችል ስላሰበች ለመሄድ ወሰነች፡፡ ከሆስፒታል እንደተነሳች ነበር ደውላ ቤት እንድትጠብቃት የጠየቀቻት፡፡፡‹‹ቀጠሮው በጣም ወሳኝ ስለሆነ  ነው ያስቸገርኩሽ፡፡››

‹‹አረ ችግር የለውም..ያንቺ እህት ማለት እኮ የእኔ እህት ነች››አለች ሜሮን፡፡

‹‹እሱስ እውነት ነው››

‹‹አዎ ደግሞም አሪፍ የምስራች አለኝ…››

‹‹እባክሽ ንገሪኝ ቀኑን ሙሉ ስጨናነቅ ነው የዋልኩት…ፈገግ ማለት አምሮኛል››

‹‹አንድ እምቅ ችሎታ ያላት እና በነርሲንግ የሰለጠነች ሞግዚት አግኝቼልሻለው›› አለቻት….ከሁለት ቀን በፊት ለሁሉም ጓደኞቾ  ስለፀጋ ነግራቸው የሰለጠነች ሞግዚት እንዲፈልጉላት አደራ ብላቸው  ነበር፡፡

‹‹አንቺ እኮ ሕይወት አድን ነሽ›› አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጯን ሳመቻት፡፡

ወደቀጠሮ ቦታ ይዛ የምትሄደቸውን ወረቀቶች ወደ ቦርሳዋ አስገባች።

‹‹ሞግዚት ማግኘት ከቻልኩ የፀጋ ዶ/ር የሰጠውን መመሪያ በሙሉ በጥንቃቄ እንዲተገበር ማድረግ እችላለው። ውዴ  ለአሁን ፀጋን ልትጠብቂልኝ ስለወሰንሽ  ደስተኛ ነኝ። ነገሮች ሁሉ ሰላም  እንደሚሆኑ አምናለው?››

‹‹ሄይ. ታውቂያለሽ እኔ  በጣም ጥሩ ጓደኛሽ  ነኝ.››

‹‹ብቃት ያለው ሞግዚት አግኝተሸልኝማ ያንን መካድ አልችልም…  በጣም ጥሩ ጓደኛ መሆን ብቻ ሳይሆን ህይወት አድንም ነሽ።››

‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ እስኪ በመጠኑ ዘና ለማለት ሞክሪ….››

ራሄል  ከወ.ሮ ላምሮት ጋር ላላት ቀጠሮ የምትጠቀምባቸውን መረጀጃዎች የያዙ ወረቀቶች እየለየች ‹‹ዘና ማለት እንኳን የምችል አይመስለኝም…ደክሞኛል… በአእምሮዬ ውስጥ ብዙ ነገሮች አሉ,››ስትል መለሰችላት፡፡ቀጥላም‹‹‹‹በፋውንዴሽን ውስጥ ነገሮች በጥሩ መንገድ እየሄዱ አይደለም ፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ለጋሾችን አጥቻለሁ አሁን የምሄድባትን ሴትዬ ከዋና ለጋሾቻችን የመጀመሪያዋ ነች….እሷን የግድ ማሳመን አለብኝ ››

‹‹ለምን ሎዛ እንድትሰራው  አታደርጊም?››

ራሄል ነገሩን በማሰብ ትንሽ ቆም ብላ ራሷን በአሉታ ነቀነቀች።‹‹ይህን ከባድ ኃላፊነት በእሷ ትከሻ ላይ መጣል አልችልም››

‹‹ስለዚህ በራስሽ ላይ ትጥያለሽ ..እሱ ችግር የለውም ማለት ነው?››

‹‹ትከሻዬ ከሷ የበለጠ ልምድ ያለው ነው›› አለች ፡፡

‹‹ጓደኛዬ ጥቂት ስራዎችን ለሌላ ሰው  ብታስተላልፊ አለም አትገለባበጥም።እና ደግሞ የህይወት ሸክማችንን የሚያቀልልን ክርስቶስ ነው….በእሱ መታመን ችግራቸንን ያቀልልናል፡፡››

‹‹እና ለምን ያቺን አሁን በስቃይ የምታለቅሰውን  ትንሽ ልጅ  እንዲህ አጎጉል አደረጋት? በኢየሱስ አላምንም ብላ ይሆን ?››በራሄል ንግግር ሜሮን  በጣም ደነገጠች፣

‹‹ራሄል .. አንቺ እኮ ከዚህ የበለጠ አስተዋይ ነሽ ››ራሄል እጇን ወደ ላይ ዘረጋች።

‹‹አዝናለሁ ስለ ኃጢአት እና ክፋት ሁሉን ነገር አውቃለሁ እናም እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር እንደሆነም አምናለው, ስለዚህ ስብከት አንዳትጀምሪኝ››

ሜሮን  የጓደኛዋን ትከሻው በፍቅር እየዳበሰች‹‹ታውቂያለሽ አይደል …?ማመን ስለማትፈልጊ ብቻ ነው. እንዲህ የምትይው…ግን እወቂ አሁንም በኢየሱስ ጥበቃ ውስጥ ነሽ …አዎ፣ በግንኙነቶች ውስጥ ህመም አለ…በሆነ ግንኙነት ተሰብረን ሊሆን ይችላል፣ ቢሆንም  ልባችንን ሁሌ ለፍቅር ክፍት መሆን አለበት ››

‹‹ደህና፣ አሁን ለልብ ጉዳዬች ጊዜ የለኝም።ደግሞ እስከአሁን ለእኔ የሚሆን ሰው አላጋጠመኝም።›› መስታወት አወጣች እና ሜካፕ እና ፀጉሯን በፍጥነት አስተካከለች።

ሜሮን ‹‹ዶ/ሩ በጣም የሚስብ ይመስለኛል››ስትል አዲስ ድንገተኛ ርዕስ ከፈተች፡፡

ራሄል የጓደኛዋን ሹፈት ችላ በማለት ቦርሳዋን አነሳችና ትከሻዋ ላይ አንጠለጠለች ፡፡

‹‹እሱ ማራኪ ነው…እንዳልኩሽ  ግን ለጊዜው ለማንም ጊዜ የለኝም ።››በማለት መለሰችላት፡፡

ራሄል ወደ በሩ ስትሄድ ሜሮን ‹‹መልካም ጊዜ ይሁንልሽ›› ብላ ጮኸች።

////
ራሄል ከሴትዬዋ ጋር እያካሄደች ያለውን ስብሰባ አንድ ሰዓት በላይ ብታሳልፍም..እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ልታሳምናት አልቻለችም፡፡

‹‹ባለቤቴ በዚህ ገንዘብ በጣም ነው የሚያምነኝ… እናም ይህን  በትክክለኛው መንገድ ማድረግ  ነው የምፈልገው፡፡››

‹‹ይገባኛል››አለች ራሄል። ነገር ግን የባለቤቷትን  እምነትን ለመጠበቅ ምርጡ መንገድ ገንዘቡን ለትክክለኛው ዓላማ ብቻ ለሚጠቀም በጎ አድራጎት መስጠት ነው።››
ወ.ሮ ላምሮት ፈገግ አለችላት፡፡

ወ.ሮ ላምሮት ራሄልን በትኩረት አየቻትና ‹‹አባትሽን ትመስያለሽ›› አለቻት። ‹‹እሱ በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚሰራ የእግዚአብሔር ፍቅር ሁልጊዜ ምሳሌ ነው.››ስትል አከለችበት፡፡

ራሄል መራራ ህመም ተሰማት። ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከአምላክ ጋር ብዙ ጊዜ አላጠፋችም። የወ.ሮዋ  ቃላት አብዝታ ወደ ጸለየችበት፣ መጽሐፍ ቅዱሷን በሰፊው ታንብበት  ወደ ነበረችበት ጊዜ አመጣት። ቤተክርስቲያን እና እምነት የመተንፈስ ያህል የእርሷ አካል ነበር። እምነቷን መልሶ ለማግኘት እና በአምላክ ላይ መታመን ለምን እንደሚያስፈልጓት አሰበች። ››

በወ.ሮ ላምሮት ፈገግ ብላ ሰዓቷን በጥበብ ተመለከተች። ለመውጣት ጊዜው ነበር፡፡

‹‹እኔ እንዳልኩት፣ እባኮት ይህን በትክክለኛው መንገድ  ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ስጡኝ..ያንን ብቻ ነው የምጠይቀው››አለች ራሄል፣

ወ.ሮ ላምሮት ከግዙፉ መኖሪያ ቤቷ ስትሸኛት ራሄል የመጨረሻ የማሳመኛ ንግግሯን ተናገረች‹‹እርግጠኛ ነኝ .. ባለቤቷት በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲቸኩሉ አይፈልግም ››

ነገር ግን ከወ.ሮዋ ፊት ምንም ነገር ማንበብ አልቻለችም  ፡፡ሴትዬዋን ለማሳመን የተቻላትን ሁሉ አድርጋለች..ግን ይሳካላት አይሳካላት መገመት ስላልቻለች በጣም ተበሳጨች ፣ መኪናውን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው…መኪናዋን አቁማ ወደአፓርታማዋ ተጠጋች… የአሳንሰሩን ቁልፍ ተጫነች እና ገባች፤ውስጥ ያልጠበቀችውን ሰው አገኘች፡፡የቆዳ ጃኬት ለብሶ ነበር። የሞተር ሳይክል ሄልሜት በእጁ ይዟል።

‹‹ሰላም. እዚህ ምን እየሰራህ ነው?››ብላ ጠየቀችው፣ እስትንፋሶ ተቆራረጠባት፡፡

‹‹በቃ ጎራ  ብዬ ከፀጋ ጋር እንዴት እየተለማመድሽ እንዳለሽ ለማየት አስቤ ነበር።››

‹‹ጥሩ አደረክ››አለችው

‹‹ወደ ውጭ ወጥተሽ ነበር?››

‹‹አዎ ጠቃሚ ስብሰባ ነበረኝ›

‹‹እንደ ሁሉም ስብሰባዎችሽ››አለ

‹‹አይዞህ አታስብ ጓደኛዬ በጣም ብቃት ያለት ሞግዚት ነች።እርግጠኛ ነኝ እሷ ከእኔ በተሻለ  ከፀጋ ጋር ትግባባለች።››ሊፍት ሲቆም ወደ ኋላ ዞር አለላት።ራሄል ቀድማ ወጣች..ተከተላት፡፡ ኮሪደሩን እንደረገጡ  የሚያለቅስ የህፃን ድምፅ በሁለቱም ጆሮ ገባ። የመጣው ከራሷ ቤት  ነው።ሁለቱም ርምጃቸውን አፈጠኑና ተከታትለው ወደቤት ገቡ ፡፡ሜሮን የምትጮኸውን ፀጋን  ተሸክማ እቤት ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ትሽከረከራለች፣ የልጁቷ ክንዶች በሜሮን  ጀርባ ላይ ተዝለፍልፋው ይታያሉ፡፡

ራሄል ቦርሳዋን ጥላ ወደ ጓደኛዋ ሮጣ ሄደች። ጸጋ ራሄልን እንዳየች ከሜሮን እቅፍ ውስጥ ተስፈንጥራ  እጇን ዘረጋች። እንባዋ በጉንጮቾ እየተንከባለሉ በመርገፍ ላይ ናቸው፡፡
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_ዘጠኝ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ



ደ ሆስፒታሉ በሚወስደው መንገድ ላይ ሞተሩን እያስጎራ በመብረር ላይ ነው፡፡ ሀሳቡ ግን አሁንም ወደኋላ እየጎተተው ነው፡፡ በዚህ የሰንበት ማለዳ ወደእነራሄል ወላጆች ቤት የሄድኩት ራሄል ፀጋን እንዴት እያስተዳደረች እንደሆነ ለማየት ብቻ ነበር። ጉብኝቱ  የህፃኗ ሐኪም በመሆኔ ያደረግኩት ነው።››ሲል ለራሱ ነገረው፡

አሁን፣ ፀጉሯን  በትና  እና የደበዘዘ ቲሸርት የለበሰች እንዲት ቆንጆ ሴት በአእምሮው ሰሌዳ ላይ ብልጭ ድርግም እያለች እየረበሸችው ነው፡፡ በባዶ እግሯ እና በሰማያዊ ጂንስዋ ምን ያህል ውብ እንደሆነች  እያሰበ ነበር፣እሷ የምትኖርበትን   ቤት እንዴት ግዙፍ እንደሆነ እና ወላጆቿ ምን ያህል ገንዘብ እንዳላቸው እያሰበ ነበር። እና የተከበረ የመኳንንት ዝርያ አለን ብለው የሚያስቡ ወላጇች እንዳሏት እያሰበ ነበር… እና ደግሞ እሱ ሰለወላጇቹ ምን ይሁኑ ምን የሚያውቀው ነገር እንደሌለም እያሰበ ነበር፡፡በዚህም ሆነ በዚያ ሀሳቡ በራሄል ዙሪያ ከመሽከርከር ሊያቅበው አልተቻለውም፡፡

ኤልያስ አሳዳጊ ወላጆቹ ስለስጋ ወላጇቹ ብዙ ጊዜ  አይናገሩም ወይም የበለጠ እንዲያውቅ አያበረታቱትም። ወደፊት ፀጋም ልክ እንደእሱ  ስለ  እናቷ እና አባቷ ማወቅ እንደምትፈልግ ገመተ።ስለ ፀጋ ማሰቡ በትክክል ወደ ራሄል መለሰው።ሸሩባ የተሰራው ጥቁር ፀጉሯ  ፊቷን እንዴት እንደአሳመረው እና ሀዘን ያጠላባቸው ጎላ ጎላ ያሉ አይኖቿ ከብለል ሲሉ እንዴት ልብን እንደሚያርዱ አሰበ። ሆስፒታል ደርሶ ሞተሩን ሲያቆም እንኳ ሀሳብን መግታት አልቻለም ነበር፡፡
///
ራሄል ትሁት ቁርስ ስትበላ ፊቷ ላይ የተዝረከረከውን በደረቅ ጨርቅ በጥንቃቄ ጠራረገችላት። እቃዎችን እያጣጠበች ሳለ ፀጋ ወደ በረንዳ በሮች ስትሄድ አየች። ሰራተኛዋ አለም ሁል ጊዜ መስኮቶቹን በሚያብረቀርቅ ንፅህና ነው የምትይዛቸው ፣ ዛሬ ግን እሷና ፀጋ ብቻቸውን ናቸው..ሰራተኛዋ የረፍት ቀኗ ስለሆነ ዘመድ ጥየቃ ሄዳለች።እቃ ማጠቧን እንዳጠናቀቀች..ትንሿን እህቷን ለማየት ወደበረንዳ ስትወጣ  የጸጋ ትንሽዬ  የእጅ ህትመቶች መስታወቱን ጠቅላላ አዳርሰውት ሌላ ቅርፅ ሰጥተውት አገኘች፡፡ መጀመሪያ   መልሳ ለማፅዳት ስትሞከር ፀጋ ከኋላዋ እየተከተለች መልሳ ስታቆሽሽባት…በመናደድ ፋንታ ከት ብላ ሳቀችና ማፅዳቱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡

‹‹ከአንድ በላይ ልጅ ያላቸው ሰዎች እንዴት በህይወት መቆየት ቻሉ?››ስትል ገረሜታዋን ገለፀች ፡፡ከፀጋ ጋር በቀጣይ ምን ማድረግ እንደምትችል አሰበች.. ።ሰዓቱን ተመለከተች, ከዚያም ወደ እሷ ተመለሰች. ወላጆቿ ዘወትር እሁድ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሄዱ ታውቃለች። ወጣት ሳለች ሁልጊዜ አብራቸው  ትሄድ ነበር፣  ነገር ግን እጮኛዋ ኪሩቤል ከሞተ በኋላ ወደቤተክርስቲያን መሄዱን እርግፍ አድርጋ ተወችው፡፡ ይህ ድርጊቷ ወላጆቿን በጣም እንደሚያበሳጫቸው ታውቃለች፣ እነሱ ስለሚፈልጉ ብቻ ነገሮችን ማድረግ እንዳለባት አታምንም። እሷ የራሷን ሕይወት እየመራች ነበር፣ እና እግዚአብሔር የህይወቷ አካል አይደለም።
ፀጋን ስትመለከት ግን በድንገት ተጨማሪ ሀላፊነት  እንዳለባት ተሰማት። በእርግጥ የሁለት ዓመት ልጅ ነበረች፣ … ስለግል  እምነቷ ለራሷ ውሳኔ ማድረግ እንደምትችል ብታምንም ለዚህች ልጅም ተመሳሳይ ነገር ማድረጉ ትክክል ሆኖ አልተሰማትም።ወላጇቾ ቢኖሩ ይዘዋት እንደሚሄዱ እርግጠኛ ነች፡፡

‹ስለዚህ ወደ ፀጋ ጎንበስ አለችና‹‹የእኔ ቆንጅዬ እህት .. ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ትፈልጊያለሽ?›› ብላ ጠየቀቻት ፡፡

ህፃኗ በደስታ እየዘለለች‹‹ቤተክርስትያን እንሂድ፣ ቤተክርስትያን እንሂድ››አለች ፡፡ ራሄልም ልብሷን ቀያይራ  ካለባበሰቻት በኋላ ወደቤተክርስቲያን ይዛት ሄደች፡፡

ራሄል የኮሌጅ ትምህርቷን እስካጠናቀቀች ድረስ ንቁ ተሳታፊ ነበረች።ሁሉ ነገር የተቀየረው እጮኛዋ ከሞት በኋላ ነው።እና አሁን የመቅደሱ ዙሪያ ስትመለከት፣ የልጅነትና የጉልምስና ትውስታዎች  ሁሉ ተግተልትለው  በአእምሯ ውስጥ ብልጭ ድርግም አሉባት። የዚህ ቤተክርስቲያን መዘምራን አባል ሆና ለረጅም አመት አገልግላለች ፤እዚህ መድረክ ላይ ወጥታ ስለጌታ የአዳኝነት ስራ ስትዘምር ትዝ ይላታል፡፡ ድምፆ ተስረቅራቂ የሚባል አይነት ስለነበር ብዙውን ጊዜ ድምጽ ማጉያውን ይዛ መዝምራኖችን የምትመራው እሷ ነበረች፡፡እጮኛዋ ኪሩቤልንም እዚሁ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው የተዋወቀችው፡፡እሱም ልክ እንደ እሷ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነበር….  ከዚያ ከመቀራረብና አብሮ ከመዋል ብዛት የፍቅር ስሜት በመሀከላቸው ተፈጠረ፡፡በቤተክርስቲያኒቷ ፊት ቃልኪዳን ተግባቡ …ሀይስኩል ጨረሱ  ..ኮሌጅ ገቡ….እስከዛን ድረስ ሁለቱም በእምነታቸው የፀኑ ወጣቶች ነበሩ…ሁሉን ነገር ሀይማኖቱ በሚያዘው እና ቤተሰቦቻቸው በሚደሰቱበት አግባብ ለማድረግ ነበር እቅዳቸው…ሰርጋቸውን ባደጉበትና ባገለገሉበት ቤተክርስቲያን አደባባይ ላይ ለማድረግ ነበር ውጥናቸውና ጉጉታቸውም…ግን ምን ሆነ ህልማቸውን ሊኖሩ ወራት ሲቀራቸው..፣ኪሩቤል ድንገት ከእሷ ጋር ወደተቀጣጠረበት ቦታ ሞተር ሳይክሉን እያበረረ ሲመጣ እየተክለፈለፍ በፍጥነት ከሚያበር መኪና ጋር ተላትሞ በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ…ይድንልኛል..መልሶ በእግሮቹ ቆሞ እንጋባላን ብላ ሆስፒታል ደረቅ ወንበር ላይ እየተኛች አንድ ወር ከግማሽ አካባቢ አስታመመችው…ግን አልተሳካም….የኪሩቤል ነፍስ ወደፈጣሪዋ ተጠርታ ሄደች..ከዛ ወዲህ ራሄል ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ሆነች…ሆስፒታል አስጠላት…የመድሀኒት ሽታ ቀፈፋት…ቤተክርስቲያንና እምነት አንገሸገሻት..የታመመ ሰው ማየት አቃታት…ይሄው አሁን ለታናሽ እህቷ  ስትል እዚህ ያደገችበት ቤተክርስቲያን ስትመጣ ቁስሏ ሁሉ ክፉኛ ተቀሰቀሰ፡፡  እና የሚቀስፍ አይነት  ህመም ተሰማት፣ ከዚሁ ሁሉ በጣም የሚገርመው ግን ለአፍታ ያህል ኪሩቤል ምን እንደሚመስል እንኳ ማስታወስ አለመቻሏ ነው ። ከሞቱ በኋላ አብዛኛዎቹን የኪሩቤልን ምስሎች በወላጆቿ ቤት  አስቀምጧቸው  ነበር እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አልተመለከቷቸውም። በጣም ተጎድታ ነበር። አሁን ምን እንደሚሰማት ግራ ተገባች።በመጨረሻም ጓዳኛዋ ሌንሳ ከወላጆቿ እና ከሁለት መንታ ልጇቾ ጋር ተቀምጣ አየች። ራሄል ከጎኗ ሾልካ ገባች።

‹‹ቤተክርስትያን መሄድ እርግፍ አድርገሽ የተውሽ መስሎኝ ነበር›› ስትል ወደጀ ጆሮዋ ቀርባ አንሾካሾከችላት፡፡
ሌንሳ   ወደኋላ ዞረችና እያወራቻት ያለችው ራሄል መሆኗን ስታውቅ በመገረም ‹‹ራሄል እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?›› ስትል ወደኋላ ተስባ አቀፈቻት፡፡

‹‹ፀጋን  ማምጣት እንዳለብኝ ተሰማኝ››ስትል የመጣችበትን ምክንያት ነገረቻት፡፡

‹‹እሺ በምንም ምክንያት ይሁን በምንም  እዚህ በመገኘትሽ  ደስ ብሎኛል.››
የሌንሳ ወላጆችም በደስታ ሰላም አሏት፡፡

ዝግጅቱ እናዳለቀ ፀጋን እንዳቀፈች እነ ለሌንሳን ተከትላ ወደአውደ ምህረቱ ሄደች…ከረጅም ጊዜ በፊት የምታውቃቸውን በጣም ብዙ የድሮ ጎደኞቾንና ወዳጆቾን አገኘች፡፡ ብዙ ሰው ለምን እንደጠፋች እየጠየቃት በመምጣቷ እንደተደሰቱ ይነግሯት ነበር፡፡
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አስር


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ


///

ከሰዓት በኋላ ራሄል የፀጋን ጋሪ መኪናው ውስጥ አስገባች  ። የዳይፐር ቦርሳውን ያዘች፣ሁሉንም ነገር እንዳላት ለማረጋገጥ ቦርሳውን ሁለቴ ፈትሸች፣ከዛ መኪናዋን ከወላጆቾ ጊቢ  አንቀሳቀሰችና ነዳችው፡፡
ወደእንጦጦ ፓርኩ ነው የነዳችው፡፡ይህ ሀሳብ ድንገት ነው የመጣባት፡፡ እንደደረሰች  መኪናዋን ፓርክ አደረገችና ..የጸጋን  ጋሪ አወረደች…እሷን አነሳችና ጋሪው ላይ አስቀመጠቻት….አነስተኛ ሻንጣ  አነሳችና በጀርባዋ አዘለች፡፡ከዛ ጋሪውን እየነዳች ወደፊት ቀጠለች… ስትራመድ የፓርኩ ፀጥታ፣የፀሀይ የሳሳ ሙቀት እና እርጥበት አዘል ንፋስ እና የዛፉ ቅጠሎች ሹክሹክታ በፅሞና እያዳመጠች ነው ።በርቀት ልጆችን ሲስቁ እና ሲሯሯጡ ይታያል። በቡድን የሚዝናኑ ሰዎች….ሳይክል የሚያበሩ ወጣቶች..ብዙ ብዙ ነገር  እያየች ፀጋን ወደ ዳገቱ እየገፋች ወደፊ ቀጠለች ፡፡

‹‹ሄሎ፣ ሄሎ›› ፀጋን  አላፊ አግዳሚው ሰላምታ እየሰጦት ያልፉ ጀመር...ራሄል መንገዱን በመከተል  ደስተኛ ሆና በአእምሮዋ ብዙ ነገር እያሰላሰለች ቀጥላለች..  ዛሬ ጠዋት ከኬሩቤል ሞት በፊትም በውስጦ የነበሩትን አስደሳች  የበረከት ስሜቶችን ቀስቅሶባታል ።
የሚገርመው፣  ቤተክርስቲያን ሆና የእግዚአብሔር ቃል ሲነገር መስማት፣ መዝሙር ሲዘመር አብራ መዘመር መቼም አደርገዋለው ብላ የምታስበው ጉዳይ አልነበረም ፡፡ ምናልባት ለእግዚአብሔር ሁለተኛ እድል ልትሰጥ ትፈልግ ይሆናል።

ራሄል ዳገቱን ጨርሳ ቁልቁለት እየወረደች ሳለ ድንገት ሳታስበው የፀጋ ጋሪ ከእጇ አሟልጮ አመለጣት …ጋሪው እህቷን ይዞ በራሱ ወደታች ተንደረደረ….ራሄል በድንጋጤ በድን ሆና ጮኸች…  ጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ባለው ሳሩ ውስጥ ምንም ጉዳት ሳይደርስባት ወደቀች ..ወደእሷ ስትንደረደር  ቀድሟት አንድ ሰው ፀጋ ጋር ደርሶ ጋሪውና አቃንቶ አነሳና እሷን ከጋሪው አንስቶ አቀፋት…..‹‹ወይኔ በጌታ!!!›› አለች ራሄል…..ያስገረማት ፀጋ ሳትጎዳ መትረፏ ብቻ ሳይሆን ከሷ ቀድሞ የደረሰላት ደ/ር  ኤልያስ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡‹‹ይሄ ሰውዬ ይከታተለኛል ማለት ነው…?እንደዛ ካልሆነማ እንደጠባቂ መልአክ  በየሄድኩበት ሁሉ በድንገት አላገኘውም ነበር››ስትል አሰበች
በፈገግታ እንደተዋጠ‹‹አይዞሽ ..ምንም አልሆነችም››ሲል ሊያበረታታት ሞከረ፡፡

‹‹ቆይ እዚህ እንገናኝ ብዬ መልእክት ልኬልህ ነበር እንዴ ?።››ስትል ጠየቀችው
‹‹አዎ እንደዛ መሰለኝ..ምነው ስላገኘሺኝ ደበረሽ እንዴ?››

‹‹ለምን ይደብረኛል….ገርሞኝ እንጂ››

‹‹ላስገርምሽ ስለቻልኩ ደስ ብሎኛል››

ፀጋ እጆቿን እያጨበጨበች።‹‹ቤተክርስቲያን ሂድን››አለችው ፡፡

‹‹ቤተክርስቲያን?››ምን ለማለት እንደፈለገች አልገባውም፡፡

‹‹ወላጆቼ ሁል ጊዜ እሁድ እሁድ ቤተክርስቲያን  ይዘዋት ይሄዱ ስለነበር  ቅር እንዳይላት ብዬ ጥዋት ይዣት ሄድኩ…እሱን ልትነግርህ ፈልጋ ነው››ሥትል አብራራችለት ፡፡

‹‹እና እንዴት ነበር?››
‹‹በእውነቱ  በጣም ጥሩ ነው.››
‹‹እሺ ..ወደሆነ ካፌ ሄደን አረፍ እንበል?የሆነ ነገር ልጋብዛችሁ?››አላት፡፡

‹‹አይ…. ለእኔ እና ለፀጋ መክሰስ አዘጋጅቼ ነበር… ቡና, ወተት እና ኩኪስ አለን.. ካፌ ከተማም ሰልችቶናል…የሆነ ለመብላት ጥሩና ጸጥ ያለ ምቹ ቦታ   ፈልጌ ነበር.››

‹‹ከዚህ የአስር ደቂቃ የእግር መንገድ በአንዳንድ በዛፎች የተከበበ  ወንበርና  ጠረጴዛ ያለበት ቦታ አለ። ለፀጋም  ቅርብ የሆነ የመጫወቻ ሜዳ አለ። ከፈለግሽ ላሳይሽ እችላለሁ።››
ራሄል የጠቀሰውን ቦታ ማግኘት ያን ያህል ከባድ እንደማይሆንባት ታውቃለች።አረ እንደውም የሚለው ቦታ በትክክል ትዝ ብሏታል፡፡ግን አብሯቸው እንዲሆን ፍላጎቷ ነው፡፡

‹‹ካላስቸገርንህ ደስ ይለኛል››አለችው፡፡

ችግር የለውም..ጥቂት ደቂቃ ስጡኝ ጓደኞቼን ተሰናብቼ ልምጣ አለና ወደኋላ ሄዶ አብረውት ከነበሩት ሶስት ጓደኞቹ ጋር በመሳሳቅ ጥቂት ቃላትን ከተለዋወጠ በኃላ ተመልሶ መጣና የፀጋን ጋሪ እየገፋ ወደተባለው ቦታ እየመራ ይወስዳቸው ጀመር፡፡

በአሁኑ ጊዜ ስለ ምንም ጥልቅ ነገር ማሰብ አልቻለም,ከእርሷ ጋር አብሮ ሄደ,  ከዚህች ሴት አጠገብ ሲሆን ለራሱ ሐቀኛ እንዳይሆን ታደርገዋለች፡፡ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ጋር መነጋገር ይከብደዋል ፣ ከፊቱ ላሉት የተወሰኑ አመታት ከሴት ራሱን ለማራቅ በተለይ ቆሚ የሆነ ግንኙነት ላለመመስረት ቁርጥ ያለ ውሰኔ ወስኖ ነበር።ለምን አሁን ራሄልን እንደሚያሳድዳት እርግጠኛ አይደለም። እሷ በተለምዶ የሚማረክባት አይነት ሴት አልነበረችም። ከመጀመርያው አንስቶ ለእሷ አሉታዊ አመለካከት ቢኖርም ፣ እሷ የሚያስደንቅ ጥንካሬ ባለቤት ሆና  በሀሳቡ ውስጥ ተሰንቅራ መቆየት ችላለች ።

‹‹ስራ እንዴትነው..ማለቴ ፋውንዴሽኑ?››ሲል ጠየቃት

‹‹ጥሩ ነው…ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ችግር አጋጥሞናል.››

‹‹ ፋውንዴሽኑ ጥሩ ለጋሾች እንዳለው ከወላጆችሽ ተረድቼ ነበር እኮ።››

‹‹በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች አዎ ትክክል ነው፣ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ አዳዲስ በጎ አድራጎት ድርጅቶችን  ገንዘብ እየጠየቁን ነው። እነዚህ ሁሉ መመርመር አለባቸው፣ ይህም ደግሞ ገንዘባቸውን ምን ላይ እንደዋለ ለማረጋገጥ ለሚፈልጉ ደንበኞችም የምናደርገው ነው። አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ በሆነ እንግዳ ምክንያት ላለፉት ጥቂት ወራት የተወሰኑ ለጋሾችን አጥተናል።››ንግግሯን   አቁማ የይቅርታ ፈገግታ ፈገግ አለችለት ።

‹‹ይቅርታ ስለ ፋውንዴሽኑ ሳወራ መጮህ እጀምራለሁ:››

‹‹አረ ችግር የለውም..አልጮኸሽም..ደግሞ ማወቅ ያለብሽ አንቺን ማዳመጥ ሁልጊዜ አስደሳች ነው።አንድ ሰው ስለ ሚወደው ነገር   ሲናገር ሁል ጊዜ በጣም ስሜታዊ መሆኑ የሚጠበቅ ነው።››ሲላት ሳቀች።

‹‹ጓደኞቼ ከስራዬ ጋር እንደተጋባው አድርገው ያወራሉ። ፋውንዴሽኑ ለእኔ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ አይረዱም። እዚያ መስራቴ ለእኔ ረድቶኛል ከጥልቅ ሀዘኔም እንዳገግም ያገዘኝ ስራዬ ነው ።››ቀና ብላ ተመለከተችው፣ ዓይኖቿ በብርታት እያበሩ ለሥራው ያላትን ቁርጠኝነት አጥርቶ ያሳይ ነበር።

የተባለበት ቦታ ደርሰው ቆሙ፡፡

‹‹በቂ  ቡና እና ተጨማሪ ስኒ አለኝ። ከእኛ ጋር ትቆያለህ አይደል?›› ስትል ጠየቀችው…  ።ለአፍታ እርግጠኛ ያልሆነች የትምህርት ቤት ልጅ ትመስላለች። ይህም ለዔሊ ግብዣዋን እንዲቀበል በቂ ማበረታቻ ሰጥቶታል።ራሄል ፌርሙሱን እና ኩባያዎቹን ስታወጣ  ትሁት ከእሱ አፈንግጣ ወደ መጫወቻ ሜዳ ሄደች።

ተመቻችተው ተቀመጡና ጫወታ ጀመሩ

‹‹ ለምን ሆስፒታሎችን ትጠያለሽ?››ሲል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡

ራሄል ራሷን ነቀነቀች፣ ለአፍታ ያህል መልስ እንደማትሰጠው አሰበ። በኋላ ግን ጉልበቷን ወደ አገጯ ሳብ አድርጋ እጆቿን አነባብራ ማውራት ጀመረች።‹‹ከስምንት አመት በፊት በሆስፒታል ውስጥ ለአንድ ወር  ከግማሽ አሳልፌያለሁ….ኪሩቤልን እግዚአብሔር እንዳገባው  የፈቀደልኝ  የልቤ ሰው መስሎኝ ነበር…አደጋው በደረሰበት ጊዜ እንደሚድን በማመን አልጋ አጠገብ ተቀምጬ ነበር። ለስድስት ሳምንታት ያህል  እግዚያብሄር እንዲያድልንኝ ያለማቆረጥ ጸለይኩ። የሆስፒታል የመተንፈሻ መሳሪያ ድምፅ እንዴት እንደሆነ ጠንቅቄ ያወቅኩት በዛን ጊዜ ነው፣ የልብ መቆጣጠሪያውንም እንደዛው። ጸሎቴ ግን ለውጥ አላመጣም…››ድምጿ በመጨረሻው ቃል ላይ ደምቆ ተሰማ፣ እና ዔሊ ታሪኩ ወዴት እንደሚሄድ ተረዳ። በእሷ ላይ ያለውን
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
_
__
///
‹‹ነይ የኔ ማር፣ ዝም በይ፣ ላደርቅልሽ እፈልጋለሁ።››ራሄል ትሁትን ከመታጠቢያ ገንዳው ውስጥ አውጥታ በፎጣው  ጠቀለለቻት።

ወደ ምትሄድበት የስብሰባ ቦታ ፀጋን መውሰድ እንዳለባት ወስናለች፡፡  ህጻኗን ዛሬ ከሰአት በኋላ  ለረጅም ሰዓት እንቅልፍ እንድትተኛ አድርጋ ስለነበር  ማታ ከሶስት ሰዓት በፊት   እንደማትተኛ ታውቃለች። ልብስ ልታለብሳት እየተዘጋጀች ሳለ ሕፃኗ ከንፈሯ ላይ በጥፊ  መታቻት። ትልቅ ሰው በጥፊ ያጠናገራት ነው የመሰላት‹‹አንቺ ትንሽ ድርዬ›› ብላ አጉተመተመች፡፡ ‹‹ምን ፈልገሽ ነው የምትደባደቢው?›› ጠየቀቻት፡፡

  በዛው ቅፅበት  የበሩ ደወል ጮኸ። ለመክፈት ፊቷን ስታዞር የራሄል እግር ይዛ  ታገለቻት ሳትወድ በግዷ ጎንበስ ብላ አቀፈቻት፡፡ አሁንም በፎጣው ተጠቅልላለች። ራሄል በረዥሙ ኮሪዶር ላይ ወርዳ የራሷን ክፍል አልፋ ወደ መግቢያ በር ቀረበች። መጥሪያው ከእንደገና ጮኸ…

‹‹መጣሁ፣ መጣሁ››ስትል ራሄል አጉተመተመች፣ አሁንም በደረጃው ላይ ነች።ከታች ስትደርስ የእብነበረድ ወለሉ ቅዝቃዜ በባዶ እግሯ ዘልቆ ተሰማት ፡፡በሩን በዝግታ ከፈተችው።ዶ/ር  ኤልያስ ነበረ፡፡

ወደ ውስጥ ስትጋብዘው ተንደርድራ ጉንጩ ላይ ተጣብቃ ልትስመው ፈልጋ ነበር…እንደምንም እራሷን ተቆጣጠረች፡፡
እሱ የፀጋ ሐኪም ብቻ ነው። እሱ የእህቷን ደህንነትን ሊቆጣጠር እናሊከታተል ብቻ ነው ወደቤታቸው የሚመላለሰው ። በማለት እራሷን ለማረጋጋት ጣረች፡፡ የዔሊ ሞቃታማ ሰማያዊ አይኖች ቀና ብላ ስትመለከት፣ውስጧ ተናወጠባት፡፡
‹‹ኤሊ ውሰደኝ…››ትሁት ጮኸች፣
ራሄል እህቷን ችላ ብላ ከኤልያስ ጋር ማውራቷን ቀጠለች፡፡‹‹አንዲት ብዙ ገንዘብ ለፋውንዴሽናችን የምትለግስ ሴት ማግኘት አለብኝ እና ምርጫ ስለሌለኝ ፀጋን ይዣት ልሄድ ነበር ያሰብኩት…ምን ትላለህ?››

‹‹ማታስቸግርሽ ከሆነ ምንም ችግር የለውም….››አላት

‹‹ እሱ የእኔም ስጋት ነው….ድፍረት ካልሆነብኝ ልትረዳኝ ትችላለህ?››

‹‹ለምን አይሆንም?እዚህ ሆኜ እንድጠብቅልሽ ነው የምትፈልጊው?››

‹‹ኮስተር አለችበት‹‹እሱም ይቻላል..ግን አብረኸን ብትሄድና እዛ ሴትዬዋ ጋር በምነጋርበት ሰዓት አንተ ፀጋን ታጫውትልኛለህ ብዬነበር ያሰብኩት…እኔም እንዲህ ሆና ይሆን ከሚል ስጋት ተገላግዬ በተረጋጋ መንፈስ ከሴትዬዋ ጋራ አወራለው››አለችው፡፡

ሳቀባት…….
በሳቁ ግራ ተጋባች‹‹ምነው ያልሆነ ነገር ተናገርኩ እንዴ?››

‹‹አይ…አሁን ኦርጂናል እናት እየሆንሽ እንደሆነ ስለታዘብኩ ነው…እዚህ ለእኔ እንኳን ቢሆን አምነሽ ጥለሻት ልትሄጂ አልፈቀድሽም…በእውነት ደስ ብሎኛል…አብሬችሁ እሄዳለው››

‹‹እሺ ይህችን ልጅ  ላልብሳት እና እኔም ለብሼ መጣን ….አስር ደቂቃ ታገሰን››

‹‹ችግር የለም..ሂዱ›› ፈቀደላቸው…ሄለን ፀጋን እንዳቀፈች ወደመኝታ ቤት አመራች፡፡ፀጋን ካለበሰች በኃላ የራሷን ልብስ ቀየረችና መስታወት ፊት ስትቆም ቅድም ፀጋ የመታቻት ከንፈሯ ቀልቶ እና አብጦ ተመለከተች….፡፡
ወደፀጋ ዞራ ልንቦጯን ዘርግታ እያሳየቻት ‹‹ውይ አንቺ ልጅ ….እይው እስኪ ያደረግሺኝን››
ፀጋ እየተመለከተቻት ሳቀችባት፡፡ራሄል ከፍሬጅ ውስጥ በረዶ አወጣችና ያዘችበት፡፡ከዛ ቀይ ሊፒስቲክ አወጣችና በስሱ በመቀባት የቀላውን ከንፈሯን ከሌላው ክፍል ጋር አመሳሰለችው፡፡
ከዛ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች ከተረዳች በኃላ ቦርሳዋን ይዛ በአንድ እጆ  የፀጋን እጅ ጨብጣ ወደሳሎን ሄደች፡፡ተያይዘው ከቤት ወጡ፡፡

ራሄል ከንፈሯን አስጨነቀች፣ ጸጋና መሀከላቸው አድርገው ወደ  ራሄል መኪና ሲያቀኑ ልክ በቅርብ የተጋቡ ባልና ሚስቶች ይመስሉ ነበር፡፡ፀጋን ከኋላ በስርዓቱ ቀበቶዋን አሰሩላትና እነሱ ገቢና ጎን ለጎን ተቀመጡ..መኪናውን የምታሽከረክረው ራሄል ነበረች፡፡
ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ነበር የተጓዙት ያሉት፡፡በፋውንዴሽኑ ውስጥ ስላሏት ችግሮች ለአንድ ሰው መንገር ፈልጋ ነበር። የሮቤል ሚስጥራዊነት አሳስቧታል።ትናንት ማታ  አነጋግራዋለች። ለምን ጥሪዋን እንዳልመለሰላት ስትጠይቀው ሞባይሉን ቤቱ ረስቶ እንደነበር  ነው የነገራት።በበጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ ያገኘኛቸውን መረጃዋች በማጠናከር ላይ ተጠምዷ ስለነበር ጊዜ አልነበረውም .. እሱ የሚፈልገው አንድ ነገር እንዳለ በግልፅ ነግሯታል….እሷም ልታምነው ፈለገች ነገር ግን አልቻለችም እና ዛሬ ከሰአት በኋላ በፋውንዴሽን ከኮምፒውተሯ ጋር ስትገናኝ፣ ሌላ ሰው የቢሮውን ኮምፒውተር ላይ እንደገባ አስተዋለች። መረጃዋን የሚበረብር ማን እንደሆነ ግራ ተጋብታለች፡፡

የአእምሮዋን ፍጭት ያነበበ ይመስል‹‹የምታናግሪው ሰው አለ?›› ስል ጠየቃት። ራሄል ወደ
‹‹ስለዚህ ነገር በተለምዶ ከአባቴ ጋር ነበር የምንነጋገረው፣ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ እንደምታውቀው በእናቴ ጉዳይ በጣም የተጠመደ ነው እና እሱን ማስቸገር አልፈልግም።››

‹‹የፋውንዴሽኑ ቦርድ እንዴት ነው? አይረዳዱሽም እንዴ?››

ራሄል አንገቷን በአሉታ ነቀነቀች። ‹‹አይ አሁን ያጋጠመን … ውስጣዊ ችግር ነው እነሱን ወደዚህ ጎትቼ ማስገባት አልፈልግም….እኔ በራሴ በምችለውን መንገድ መፍትሄ መፈለግ አለብኝ››

‹‹ሁሉንም ነገር በራስሽ ብቻ ማድረግ የለብሽም››ኤሊ ተቃወማት ።በዚህ ጊዜ የሚሄዱበት ቦታ ደርሰው መኪናዋን እያቆመች ነበር፡፡
ትንሽ ሳቅ ብላ‹‹በቅርብ ጊዜ ሁሉንም ነገር በራሴ የማደርገው ይመስላል››ስትል ቦርሳዋን አንጠልጥላ ከመኪናዋ ወረደች፡፡ራሄል ከመኪናው ጎን በመጣችበት ጊዜ ኤሊያስ ፀጋን ከታሰረችበት ቀበቶ እየፈታት ነበር። የዳይፐር ቦርሳውን ለራሔል ሰጣት እና በሩን ዘጋው።  ራሄል ወደ ወ.ሮ ላምሮት መግቢያ ደረጃ ሲወጡ‹‹ልክ  እንደ ትንሽ ቤተሰብ እንመስላለን››ስትል አሰበች።

መግቢያ በራፉ ላይ ደረሱና ደወሉን ተጫኑት፡፡ ‹‹ማግባት ምን አይነት ጣዕም ሊኖረው  ይችላል?››እራሷን ጠየቀች፡፡ ጋብቻ ከኪሩቤል  በኃላ ያልተጠቀመችበት ቃል ነበር።የስሙ ትዝታ የደስታ ስሜት እንዲሰማት አደረጋት፣ ከዚያም የታማኝነት መጉደል ውስጧን ሲያንቀጠቅጣት ተሰማት። እንዲህ ያሉ የቀን ህልሞችን እንድታልም ስውር ኃይል የነበረው ኪሩቤል ብቻ ነበረች። ከዚህ በፊት ወይም በኋላ ማንም ሌላ ሰው ያንን  ስሜት ሊቀሰቅስባት አልቻለም ።
ራሄል ድጋሚ ደወሉን ልትደውል ስትል በሩ በራሱ ተከፈተ። ራሄል ወደ አንድ ትልቅ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ገባች ወዲያው ጥርት ያለ ሰማያዊ ቀሚስ የለበሰች ሴት ተቀበለቻት።

‹‹ወ/ሮ ላምሮት ከኋላ ባለው አትክልት ስፍራ እየጠበቀችሽ ነው።››በማለት ዘወር ብላ ወደ ሌላ በር መራቻቸው፡፡ ወደ ዔሊ ተጠግታ በሹክሹክታ  ‹‹ፀጋ ከስርህ እንድትርቅ አትፍቀድላት። ››ስትል ተናገረች፡፡ፈገግ አለላት….በፊት ፀጋን በተመለከተ እንዲህ አድርጊላት… ይሄንን ተጠንቀቂላት… እያለ የሚያጨናንቃት እሱ ነበር..አሁን ግን ይሄው በተቃራኒው ለእሱ መመሪያ እየሰጠችው ነው፡፡እያሳየች ባለችው ለውጥ በውስጡ እርካታ ተሰማው፡፡
ወ.ሮዋ ከተቀመጠችበት መድረክ መሳይ ውብ ቦታ ባሻገር በሁለት በኩል በጡብ ግድግዳ የተከበበ አበባ ሞልቶ ነበር። ወ.ሮ ላምሮት በትልቅ ዣንጥላ በተከለለ የመስታወት ጠረጴዛ ጎን ከተቀመጠችበት ልዩ ወንበር ተነስታ ‹‹ ጤና ይስጥልኝ ራሄል …በድጋሚ እንኳን ደህና መጣሽ ›› አለቻት ፡፡
#የእግዜር_የአደራ_ልጅ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ



ከወ.ሮ ላምሮት ቤት እንደተመለሱ ቀጥታ ወደራሄል  ወላጇቾ ቤት ነው የሄዱት፡፡ኤልያስ ቤት ድረስ አብሯቸው የመጣው በሁለት ምክንያት ነው…አንድም ሊሸኛቸው ሲሆን ሌላው ግን ጥዋት ከቤት ወጥቶ አብሯቸው ሲሄድ  ሞተር ሳይክሉን እዛው ጥሎ ስለነበረው የሄደው እሱን ለመውሰድ ነው…"ካለበለዚይ ጥዋት ወደስራ ለመግባት ታኪሲ ፍለጋ መጋፋት ሊጠበቅበት ነው…ያ ደግሞ በጣም የሚጠላው ነገር ነው፡፡

ደርሰው  ራሄል መኪናውን ፓርክ አድርጋ እንዳቆመች እሱ ፈጠን ብሎ ወረደና ፀጋን አንስቶ አቀፋት..ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዷት ስለነበረ ሲያቅፍት  ልጥፍ አለችበት፡፡ራሄል ቦርሳውን አንስታ አንጠለጠለችና ተከተለቻቸው እና ወደ ግዙፍ ቤት ተከታለው ሲገቡ ጥዋት ተሰምቷት የነበረ ስሜት ተመልሷ ተሰማት…ባሏ… ተወዳጅ ልጇን አቅፎ ወደቤት ሲገቡ….ሀሳቡ የደስታ  ውስጧ በደስታ ስሜት እንዲጥለቀለቅ ስላደረጋት ‹‹እንዴት ደስ ይላል››ስትል በለሆሳሳ አንሾካሾከች፡፡ከፊት ቀደመችና ሳሎኑን ሰንጥቃ እየመራች ወደፀጋ ክፍል ይዛው ሄደች… ቶሎ ብላ ብርድ ልብሱን ገለጠችለት…ቀስ ብሎ አስተኛትና ተጋግዘው አለባበሳትና ቆመ…ተከትላው ቆመች…በመሀከላቸው ያለው ርቀት ከአንድሜትር አይበልጥም…አንደኛው ሌለኛው ላይ አፍጥጧል….በሚገርም ሁኔታ የትንፋሽ ማጠር አጋጠማት. …ቀስ እያለ ተጠጋትና እጇቹን በወገቧ ላይ አሳረፈ፡፡
ውርር የሚያደርግ ጥሩ ስሜት ተሰማት…ከዛ በምን ፍጥነት እንደሆነ ሳታውቅ ከንፈሮቹ በእሷ ከንፈር ላይ አረፉ …የራሄል አይኖች ተዘጉ፤ እና ለአፍታ ድንጋጤ ተሰማት ፣  እጆቹ በወገቧ ዙሪያ  ተጠመጠሙባት እና ወደራሱ ጎትቶ አስጠጋት። ራሄል ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ  ሙሉ በሙሉ በቀጣይ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር የማወቅ ጉጉት ተሰማት። የበለጠ ልትለጠፍበትና ልትደገፍበት ፈቀደች፡፡ ‹‹ይህ ጥሩ ሥነ ምግባር አይደለም?››በውስጧ ነበር ያሰበችው… በድንገት የከበደውን ከባቢ አየር ማቅለል ፈለገች። ለብዙ ዓመታት ሳትወድቅ ከቆየችበት ቦታ ለመመለስ ተፍጨረጨረች።

‹‹የእህቴን  ሐኪም መሳም ?››ከእቅፉ ሳትወጣ  የሹክሹክታ ድምፅ አሰማች።ወደፊቷ የተደፋውን  ፀጉሯን ወደኃላ በመመለስ አስተካከለላት፡፡ከዚያም ,  ቀስ ብሎ ከከንፈሯም ከአካሏ ተላቀቀ እና እራቅ አለ።

‹‹ ፀጋ ቅሬታ እንደማታቀርብ አምናለው››አለችና  ዓይኗን በእፍረት ደፍች፡፡  ለእሱ ያላትን መስህብ በውስጧ መቅበር እስከቻለች  ድረስ፣ እራሷን ከእሱ ለይታ ማቆየት እስከቻለች ድረስ፣ እነዚህን አዳዲስ እና አደገኛ  ስሜቶች መቋቋም እንደምትችል ታስብ ነበር።አሁን ግን?በጣም ለረጅም ጊዜ የናፈቀችውን ነገር ቀምሳለች። ከንፈሯ ላይ መች ተጠግቶ እንደተጣበቀባት  እንኳን አላወቀችውም። ፍቃዷን እና ሙሉ  ስሜቷን ለዚህ ሰው እስክትሰጥ ቅፅበት ድረስ  ልቧን በኪሩቤል የመቃብር ቦታ ለዘመናት ቀብራው ነበር፡፡ በደረሰባት ኪሳራ ተበሳጭታ ስለነበረ  ራሷን ዳግመኛ እንደዚህ ላለ ሁኔታ ለማጋለጠ ፈፅሞ እንደማትፈቅድ ቃል ገብታ ነበር። አንድን ሰው በጥልቀት ለመንከባከብ መፍቀድ ራስን ነገ በድንገት ለሚመጣ ህመም ማመቻቸት እንደሆነ ህይወት አስተምራታለች።ከዛ ስቃይ ለማገገም እና እንደገና ወደህይወት  ለመመለስ ዓመታት ፈጅቶባታል።

‹‹ይሄ ጉዳይ  በጣም ያስፈራኛል።››አለችው፡፡
አገጯን በአውራ ጣት ዳባበሳት እና ‹‹ምንም አይደለም እኔም  እፈራለሁ:: ግን  ፍርሀታችንን ለማለስለስ ብዙ ጊዜ አለን››አለና ሊያበረታታት ሞከረ፡፡
በረጅሙ ተነፈሰች፣ ከዚያም ፈገግ አለች።

ጭንቅላቷ ላይ ሳማትና ከዚያም በሹክሹክታ ‹‹ባዬ ራሄል››በማለት ክፍሉንም  ቤቱንም ለቆ ወጣ ።ራሄል እስከሳሎን ተከተለችውና  ከኋላው በሩን ዘጋች፡፡ የሞተር ሳይክሉን ድምፅ በመኪና መንገዱ ላይ ሲንደቀደቅ ሰማች። ጭንቅላቷን ቀዝቃዛው  መስታወት ላይ አስደገፈች፡፡ …በድንገት መጸለይ እንዳለባት ተሰማት።‹‹ጌታ ሆይ እሱን ጠብቀው›› አለች ‹‹ራሷን ለሌላ ሰው በዚህ መንገድ እከፍታለው ብላ ፈፅሞ አስባ አታውቅም ነበር? የፀጋ የታፈነ ጩኸት  ተሰማት…ራሷን ከተደገፈችበት  መስታወት  ቀና አደረገች እና ተንቀሳቀሰች…ከዛ ወደ ፀጋ ሄደች። እህቷን ለመከታተል ወደ ደረጃው እየሮጠች ስትሄድ፣ ቀድሞ የነበረባትን ስሜት እየሰመጠ እንደሆነ ተረዳች።
///
ዔሊያስ የቤቱን ዙሪያ ገባ ተመለከተ። ምንም ያማረ ነገር የለም። በራሱ ቤት ውስጥ በራሱ ሶፋ ላይ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም፣ አእምሮው ከአንድ በሰአት በፊትና በተለያት ሴት ላይ ተጣብቆ ነበር።ከአንድ ሰአት በፊት የሳማት ሴት አሁንም ልቡ ውስጥ እየተገላበጠች ነው።እንደዛ ያለ ድንገተኛ እርምጃ እንዲወስድ ያነሳሳው ምንድን ነበር?ቢያስብ ቢያስብ ሊገለፅለት አልቻለም፡፡
እረፍት አጥቶ ከሶፋው በመነሳት ቢንያም ወደተኛበት ክፍል ተራመደ… ሀሳቡ  ዋና መኝታ ቤቱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ማለቅ እንዳለበት ሊነግረው ነበር ። ነገሮች እንዳሰበው ሚሄዱ ከሆነ እና የገንዘብ እጥረት ካላጋጠመው ቤቱ በስድስት ወር ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይፈልጋል። በእቅዱ መሰረት ቤቱን ካጠናቀቀ በኃላ ቀጣዩ እቅዱ አዲስ መኪና መግዛት ነው።  እና ከዚያ ምናልባት ይህንን ንፁህ እና በስርዓት የተቀነበበ  ህይወቱን የምትካፍለው ሴት መፈለግ ይኖርበት ይሆናል። ከአመታ በፊት  እቅዱን  በዚህ መንገድ በቅደም ተከተል ሲያስቀምጥ ሁሉም ነገር እንከን የለሽ እንደሆነ እርግጠኛ ነበር፡፡  ነገር ግን ያ ራሔል ከፊቱ ከመጋረጧ በፊት ነበር ።

የወንዱሙን ክፍል ለመክፈት እጄታውን ከያዘ በኃላ ሀሰቡን ቀየረ…ራሴ ተረብሼ ለምን እሱን እረብሸዋለው..በማለት ወደኃላ ተመለሰና ወደራሱ መኝታክፍል ገባ፡፡የልብሱን መሳቢያ ከፍቶ ከአሳዳጊ ወላጆቹ ቤት ያመጣውን የስጋ ወላጇቹን የፎቶ ሳጥን አወጣ ፡፡ራሄል ያቀረበችለትን ሀሳብ በድጋሚ አሰበበት።  ምናልባት አሳዳጊዎቹ ይሄንን የወላጆቹን ፎቶ ከእሱ ለማራቅ ጥሩ ምክንያቶች ነበሯቸው።በወላጆቹ ፊት ላይ የራሱን አሻራ ለማግኘት እየሞከረ ፎቶውን አገላብጧ ተመለከተ። አገጩን በእናቱ፣ ዓይኖቹ በአባቱ መልክ ላይ በጨረፍታ የተመለከተ መስሎት ነበር። ወይም ምናልባት ምኞት እንደዛ ስለሆነ ይሆናል፡፡ ፡፡እሱ እንደ አብዛኛው የማደጎ ልጆች ፣ስለ ወላጆቹ  ይበልጥ ለመማር  እና ለማወቅ ፍላጎት ነበረው ።እሱን በተመለከተ  በህፃናት ማሳደጊያ ተቋሙ ውስጥ ያለው ፋይል ውድ የሆኑ ጥቂት መረጃዎችን የያዘ ሲሆን አንዳንድ ነገሮችን እንዲያውቅ አድርገውታል፡፡ታዲያ ለምን መርካት አልቻለም?

ራሄል የማንቂያ ሰዓቱን ላይ ባለማመን አፈጠጠች።እንቅልፍ አልወስዳት ብሎ  ከግራ ወደቀኝ እየተገላበጠች ለአንድ ሰአት ተሰቃየች… የሰዓቱ መንቀርፈፍ የዘለአለም መሰላት። ደጋግማ  ከኤሊ ጋር ስታጫውተው የነበረውን ትዕይንት አዲስ እንደወጣ ተወዳጅ ፊልም ደጋግማ በምልሰት በማሰብ  አጣጣመችው፣ የከንፈሮቹን ንክኪ እንደገና ተሰማት።መላልሳ ባሰበችው ቁጥር በእያንዳንዱ ትውስታ  አዲስ ስሜት ይሰማት ነበር። በቀጣይ ምንድነው የሚሆነው….?እራሷን ትጠይቃለች….አእምሯዋ ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ግራ መጋባት ውስጥ  አሽቀንጥሮ ይጥላታል፡፡
ያለፈውን የልቧን ጭለማ ጓዝ  እንዴት መልቀቅ እንዳለባት እስከአሁን አላወቀችም፣ አልደፈረችም።