#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ሺሕ ዓመት ንገሥ።"
ምንትዋብ፣ አፄ በካፋ ወደ መሠሪ እንድትመጣ ሲልኩባት፣ ሕይወቷ
ዳግም ተለወጠ። ለጥቂት ቀናት መሠሪ ሱባዔ ገብተው ስለነበር
ጨርሰው ነው ብላ አስባለች። ከእናቷና ከአያቷ ጋር መሠሪ ስትደርስ፣የበካፋ ታማኝ እልፍኝ አስከልካዮች ቴዎድሮስ፣ ገላስዮስና ድንጉዜ ዐይኖቻቸው ደም መስለዋል። እጅ ነስተዋት ስትገባ መሠሪ ከብዶታል፤
ጨላልሟል። ከወትሮው ጠባብ ሆኖባታል።
አፄ በካፋ ከተኙበት ኣልጋ ራስጌ የነፍስ አባታቸው አባ ዐደራ
መስቀላቸውን ይዘው ቆመዋል። ኒቆላዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ ግርጌ
አቀርቅሮ ቆሟል። ምንትዋብ ርምጃዋን ገታ አድርጋ ክፍሉንም
ሰዎቹንም ቃኘች።
ነገሩ አላምር አላት። መንፈሷ ተረበሸ። ሱባዔ ላይ የነበሩት ባሏ ምን እንደደረሰባቸው መገመት አቃታት። ወደ አልጋቸው መራመድ ፈልጋ እግሮቿ አልታዘዝ አሏት፤ ትንፋሽ አጠራት። ልቧ ደረቷን ሲደልቅ እንደ ማጥወልወል አላት። ሐውልት ይመስል ደርቃ ቀረች። ዐይኗ ኒቆላዎስን ኣልፎ ንጉሠ ነገሥቱ ላይ ሲያርፍ፣ ፊታቸው ተሸፍኗል።
ዕለቱ ማክሰኞ፣ ቀኑ መስከረም አስራ ስድስት ዓመተ ምህረቱ 1723 ነው። እኒያ ቅኔ የሚቀኙት፣ መንፈሳዊ መጻሕፍትን የሚፈትሹት፣ አደን የሚወዱት፣ ለሃገራቸው ፊደላት ጥብቅና ቆመው፣ “ፊደል አሳስቶ የጻፈ
እጁ ይቆረጣል” ብለው አዋጅ የጣሉት፣ ሥነ-ጥበብ እንዲዳብር፣ ቃላት እንዲበለፅጉ የጣሩት፣ በወባ ንዳድ ርደው እንደተራ ሰው ባላባት ቤት መደብ ላይ የተኙት፣ ላይ ታች እያሉ ያመጸውን ያስገበሩት፣ ያጠፋውን አይቀጡ ቅጣት የቀጡት፣ እንደ ቀደምት ነገሥታት የሃይማኖት ክርክር
ያከራከሩትና አሻራቸውን ለመተው የራሳቸውን ግንብ የገነቡት አፄ
በካፋ በነገሠ በዘጠኝ ዓመት ከዐራት ወራቸው፣ ምንትዋብን ባገቡ በሰባት ዓመታቸውና በተወለዱ በሰላሳ ሰባት ዓመታቸው ሕይወታቸው
አልፏል።
“ምንድርነው? ጃንሆይ ምን ሁነዋል?” አለች፣ ምንትዋብ፣ ድምጾ ይርበተበታል ።
ተጠጋቻቸውና ቡሉኮውን ከፊታቸው ላይ ገለጥ አደረገችው።አፍንጫቸው ጫፍ ላይ ደም አየች፤ መላ ሰውነቷ ራደ። ኒቆላዎስ ላይ አፈጠጠች።
“ድንገት ነው የሆነው። ባፍ ባፍንጫቸው ደም ፈሰሰ... ምንም ያህል አልቆዩ ዐረፉ” አላት።
ራሷን በሁለት እጆቿ ይዛ “ኡኡኡኡ...” አለች። እናቷና አያቷ
ፈጠን ብለው ግራና ቀኝ ደገፏት።
“ምነው ሳትነግሩኝ? ስለምንስ ከፋችሁብኝ?” እያለች ጮኸች።
መሬት ላይ ተንከባለለች።
ያን ጊዜ እናቷና አያቷ አብረዋት ጮሁ። እንደ እሷ መሬት
ላይ ተንከባለሉ። መሠሪ ጩኸት በጩኸት ሆነ። ዋይታ በረከተ።
ምንትዋብ ለያዥ አስቸገረች። እነግራዝማች ኒቆላዎስ ተጨነቁ፡
ለቅሶው እንዳይሰማ። የቤተመንግሥት ባለሟሎች እንኳን እንዲሰሙ አልተፈለገም።
ምንትዋብ የምትሆነው ጠፋት። ከቶውንም የደረሰውን ማመን
አቃታት። አጎንብሳ፣ “ወዮ እኔ! ይብላኝ ለኔ” እያለች እንባዋን አዘራች።ኒቆላዎስና አባ ዐደራ ግራና ቀኝ እጆቿን ይዘው እንድትቀመጥ ግድግዳ ተጠግቶ ወደ ተቀመጠ ወንበር ሊወስዷት ሞከሩ።
“ተዉኝ... ተዉኝ! ለባሌ ላልቅስ።
ተዉኝ!” እያለች እሪ አለች።
“እቴጌ ባክዎ ለቅሶዎ እንዳይሰማ” አሏት፣ አባ ዐደራ።
“ይሰማ ይሰማ! አገር ይስማ! እኔ አለባል ልዤ አላባት መቅረታችንን...አገር ይስማ... ወዮ እኔ...ወዮ ልዢ ።”
እነኒቆላዎስ እንደ ምንም አባብለው አስቀመጧት። አንዴ ንጉሠ ነገሥቱ የተኙበትን አልጋ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጣራውን ደግሞም ወለሉን እያየች እንባዋ ረገፈ። ሐዘኗ መሪር ሆነ። የደረሰባትን ድንገተኛ ሐዘን
ጫንቃዋ መቋቋም የሚችል አልመስል አላት። ዓለም አስፈሪ ቦታ ሆነችባት። ሕይወቷ ላይ የሐዘን ጥላ አጠላችበት። የመኖር ተስፋዋን ሸረሽረችው። ትናንት ማሾ እያበራች ፈለጓን የተከተለችው መሬትም
ድንገት ጨለመችባት።
አልጋ ባልጋ የመጣው የሕይወቷ መንገድ ፍጻሜው የተቃረበ
መሰላት።
እንደገና ጩኸት ጀመረች። እነኒቆላዎስ ተደናገጡ። የእሷም
ሆነ የእናቷና የአያቷ ጩኸት እንዳይሰማ ፈሩ፤ ለማባበል ሞከሩ፤ አልሆነላቸውም። ምንትዋብን ብዙ ኃላፊነት እንደሚጠብቃት ኒቆላዎስ
ለማስረዳት ቢሞክር አልሰማ አለችው።
“ባሌ ኸሞቱ ገዳም ገብቸ መመንኮስ አለብኝ” አለችው።
እንባዋ ደረቷ ላይ ይወርዳል። ያቺ ፀዳል የመሰለች ሴት ፊቷ ድንገት
ጨለማ ለብሷል። ከመቅጽበት ዕድሜዋ ላይ ዓመታት የተጨመሩ
መስለዋል። ከዐይኗም ከአፍንጫዋም የሚወርደው ፈሳሽ አልቃሻ ሕፃን ልጅ አስመስሏታል።
ኒቆላዎስና አባ ዐደራ ተረበሹ። እናቷና አያቷ ለቅሷቸውን አቋርጠው በድንጋጤ ተመለከቷት።
“አዎ... ኸዝኸ በኋላ ምን ዓለም አለኝ? እኔም እንደ ባለቤቴ መሬት
እስትገባ ዓለሜ ምናኔ ነው። እሳቸው ሙተው እኔ እንዴት ባለም
ኖራለሁ? ልዤን ይዤ ኸዳለሁ” እያለች ጮኸች።
ኒቆላዎስ፣ “የለም የለም፤ እኼማ አይሆንም” አላት፣ ተጠግቷት።
“ደሞስ ምናኔ ማን ያደርስሻል? የጃንሆይ ጠላቶች ወይም ወህኒ
አምባ ያሉ ደጋፊዎች ምንገድ ላይ ጠብቀው አንቺንም ልዥሽንም
ይገድሏችኋል። ባይገድሏችሁ ስንኳ መውጫና መውረጃ የሌለው ወህኒ አምባ ወስደው ያስሯችኋል። ገዳም ብትገቢም ጃንሆይ ቅባት ሃይማኖት
ተከታይ ነበሩ ተብለው ስለሚጠረጠሩ እዚያ ብዙ የተዋሕዶ መነኩሴ ጠላቶች አሏቸው፤ ይጣሉሻል” አላት።
እሷ ግን፣ “በቁስቋሟ ተዉኝ! ተዉኝ” እያለች እጆቿን እያርገበገበች ተማጸነቻቸው።
ያን ጊዜ አባ ዐደራ፣ “እቴጌ መቸም መቀበል እንጂ ምን ማረግ ይቻላል? ኸሞት ሚቀር የለ። አሁን እርስዎ እንደዝኸ ሲሆኑ ሳንዘጋጅ የጃንሆይ መሞት የተሰማ እንደሁ ሁከት ይነሳል። ወህኒ ያሉትም እግረ ሙቃቸውን ፈተው ይመጣሉ። ንጉሥ ሞተ ሲባል ሚሆነውን እናውቃለን። ባክዎ ይጠንክሩልን” እያሉ ተለማመኗት።
ዮልያናም፣ “የኔ ልዥ! ባክሽ ጠንክሪ። እንደዝህ መሆን ደግ ማዶል” እያሉ እንባዋን በነጠላቸው ጠራረጉላት፣ የራሳቸውን ለመግታት
እየታገሉ።
“ልጄ በጡቴ ይዤሻለሁ! በኢያሱ ይዠሻለሁ! በምትወጃት በቁስቋም ማርያም ይዠሻለሁ! በምትወጃቸው ባባትሽ አጥንት ይሻለሁ በርቺልኝ” እያሉ እንኰዬም ሙሾ እንደሚያወርዱ ሁሉ እጃቸውን ወደ ኋላ አድርገው እንባቸውን እያዘሩ ለመኗት።
እሷ ግን እንባዋን መግታት አቃታት፤ አልጽናና አለች።
ኒቆላዎስ አንዴ እንድታዳምጠው ለምኗት የንጉሠ ነገሥቱን ኑዛዜ
ቃል በቃል ነገራት።
“ምን እንደተሰማቸው አላወቅሁም ብቻ እኔን አስጠሩኝ። ኒቆላዎስ...
ዐደራ ምልህ ልዤን... አሉኝ፣ ድምጣቸው እየተቆራረጠ። ልዤን
ኢያሱን እንድታነግሥልኝ። ለነገሥታት ሚደረገውን ሥርዐት ሁሉ... ቅባዓ ንጉሡንም ዘውዱንም... አርገህ እንዲነግሥልኝ። እናቱ ምንትዋብ
ብልህ ናት ትርዳው፤ ኸጎኑ ትሁን። እሷ አገር መምራትና... ማስተዳደር
ትችላለች። አርቆ አስተዋይና እዝጊሃር የባረካት ሰው ናት። አገሬን... አገሬን ኸልዣችን ጋር ሁና፣ ተባህር እስተ ባህር ታስተዳድር። አገሬ.. ምንም ዓይነት በደል እንዳይፈጠምባት። እኔ የዠመርሁትን ሁሉ. አጠናክረሽ ቀጥይ፤ በዐጸደ ነፍስ ኹኜም አልለይሽም በልልኝ። ሁላችሁም ቃሌን ንገሩልኝ…. ዐደራ” ብለው አንቺን እንድንጠራላቸው
ሲጠይቁ፤ ደም ባፍ ባፍንጫቸው ያለማቋረጥ ወረደ። ግዝየም አላገኙ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች።”
ምንትዋብ፣ ተናግሮ ሲጨርስ ሳግ እየተናነቃት ጣሪያውን፣
ግድግዳውን፣ ወለሉን፣ ሁሉንም በየተራ ተመለከተች። እነሱ ምን
እያሰበች እንደሆነ መገመት አቃታቸው። አንዴ እርስ በእርስ እየተያዩ ሌላ ጊዜ እሷን እያዩ ከአፉ የሚወጣውን ለመስማት ተጠባበቁ።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ሺሕ ዓመት ንገሥ።"
ምንትዋብ፣ አፄ በካፋ ወደ መሠሪ እንድትመጣ ሲልኩባት፣ ሕይወቷ
ዳግም ተለወጠ። ለጥቂት ቀናት መሠሪ ሱባዔ ገብተው ስለነበር
ጨርሰው ነው ብላ አስባለች። ከእናቷና ከአያቷ ጋር መሠሪ ስትደርስ፣የበካፋ ታማኝ እልፍኝ አስከልካዮች ቴዎድሮስ፣ ገላስዮስና ድንጉዜ ዐይኖቻቸው ደም መስለዋል። እጅ ነስተዋት ስትገባ መሠሪ ከብዶታል፤
ጨላልሟል። ከወትሮው ጠባብ ሆኖባታል።
አፄ በካፋ ከተኙበት ኣልጋ ራስጌ የነፍስ አባታቸው አባ ዐደራ
መስቀላቸውን ይዘው ቆመዋል። ኒቆላዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ ግርጌ
አቀርቅሮ ቆሟል። ምንትዋብ ርምጃዋን ገታ አድርጋ ክፍሉንም
ሰዎቹንም ቃኘች።
ነገሩ አላምር አላት። መንፈሷ ተረበሸ። ሱባዔ ላይ የነበሩት ባሏ ምን እንደደረሰባቸው መገመት አቃታት። ወደ አልጋቸው መራመድ ፈልጋ እግሮቿ አልታዘዝ አሏት፤ ትንፋሽ አጠራት። ልቧ ደረቷን ሲደልቅ እንደ ማጥወልወል አላት። ሐውልት ይመስል ደርቃ ቀረች። ዐይኗ ኒቆላዎስን ኣልፎ ንጉሠ ነገሥቱ ላይ ሲያርፍ፣ ፊታቸው ተሸፍኗል።
ዕለቱ ማክሰኞ፣ ቀኑ መስከረም አስራ ስድስት ዓመተ ምህረቱ 1723 ነው። እኒያ ቅኔ የሚቀኙት፣ መንፈሳዊ መጻሕፍትን የሚፈትሹት፣ አደን የሚወዱት፣ ለሃገራቸው ፊደላት ጥብቅና ቆመው፣ “ፊደል አሳስቶ የጻፈ
እጁ ይቆረጣል” ብለው አዋጅ የጣሉት፣ ሥነ-ጥበብ እንዲዳብር፣ ቃላት እንዲበለፅጉ የጣሩት፣ በወባ ንዳድ ርደው እንደተራ ሰው ባላባት ቤት መደብ ላይ የተኙት፣ ላይ ታች እያሉ ያመጸውን ያስገበሩት፣ ያጠፋውን አይቀጡ ቅጣት የቀጡት፣ እንደ ቀደምት ነገሥታት የሃይማኖት ክርክር
ያከራከሩትና አሻራቸውን ለመተው የራሳቸውን ግንብ የገነቡት አፄ
በካፋ በነገሠ በዘጠኝ ዓመት ከዐራት ወራቸው፣ ምንትዋብን ባገቡ በሰባት ዓመታቸውና በተወለዱ በሰላሳ ሰባት ዓመታቸው ሕይወታቸው
አልፏል።
“ምንድርነው? ጃንሆይ ምን ሁነዋል?” አለች፣ ምንትዋብ፣ ድምጾ ይርበተበታል ።
ተጠጋቻቸውና ቡሉኮውን ከፊታቸው ላይ ገለጥ አደረገችው።አፍንጫቸው ጫፍ ላይ ደም አየች፤ መላ ሰውነቷ ራደ። ኒቆላዎስ ላይ አፈጠጠች።
“ድንገት ነው የሆነው። ባፍ ባፍንጫቸው ደም ፈሰሰ... ምንም ያህል አልቆዩ ዐረፉ” አላት።
ራሷን በሁለት እጆቿ ይዛ “ኡኡኡኡ...” አለች። እናቷና አያቷ
ፈጠን ብለው ግራና ቀኝ ደገፏት።
“ምነው ሳትነግሩኝ? ስለምንስ ከፋችሁብኝ?” እያለች ጮኸች።
መሬት ላይ ተንከባለለች።
ያን ጊዜ እናቷና አያቷ አብረዋት ጮሁ። እንደ እሷ መሬት
ላይ ተንከባለሉ። መሠሪ ጩኸት በጩኸት ሆነ። ዋይታ በረከተ።
ምንትዋብ ለያዥ አስቸገረች። እነግራዝማች ኒቆላዎስ ተጨነቁ፡
ለቅሶው እንዳይሰማ። የቤተመንግሥት ባለሟሎች እንኳን እንዲሰሙ አልተፈለገም።
ምንትዋብ የምትሆነው ጠፋት። ከቶውንም የደረሰውን ማመን
አቃታት። አጎንብሳ፣ “ወዮ እኔ! ይብላኝ ለኔ” እያለች እንባዋን አዘራች።ኒቆላዎስና አባ ዐደራ ግራና ቀኝ እጆቿን ይዘው እንድትቀመጥ ግድግዳ ተጠግቶ ወደ ተቀመጠ ወንበር ሊወስዷት ሞከሩ።
“ተዉኝ... ተዉኝ! ለባሌ ላልቅስ።
ተዉኝ!” እያለች እሪ አለች።
“እቴጌ ባክዎ ለቅሶዎ እንዳይሰማ” አሏት፣ አባ ዐደራ።
“ይሰማ ይሰማ! አገር ይስማ! እኔ አለባል ልዤ አላባት መቅረታችንን...አገር ይስማ... ወዮ እኔ...ወዮ ልዢ ።”
እነኒቆላዎስ እንደ ምንም አባብለው አስቀመጧት። አንዴ ንጉሠ ነገሥቱ የተኙበትን አልጋ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጣራውን ደግሞም ወለሉን እያየች እንባዋ ረገፈ። ሐዘኗ መሪር ሆነ። የደረሰባትን ድንገተኛ ሐዘን
ጫንቃዋ መቋቋም የሚችል አልመስል አላት። ዓለም አስፈሪ ቦታ ሆነችባት። ሕይወቷ ላይ የሐዘን ጥላ አጠላችበት። የመኖር ተስፋዋን ሸረሽረችው። ትናንት ማሾ እያበራች ፈለጓን የተከተለችው መሬትም
ድንገት ጨለመችባት።
አልጋ ባልጋ የመጣው የሕይወቷ መንገድ ፍጻሜው የተቃረበ
መሰላት።
እንደገና ጩኸት ጀመረች። እነኒቆላዎስ ተደናገጡ። የእሷም
ሆነ የእናቷና የአያቷ ጩኸት እንዳይሰማ ፈሩ፤ ለማባበል ሞከሩ፤ አልሆነላቸውም። ምንትዋብን ብዙ ኃላፊነት እንደሚጠብቃት ኒቆላዎስ
ለማስረዳት ቢሞክር አልሰማ አለችው።
“ባሌ ኸሞቱ ገዳም ገብቸ መመንኮስ አለብኝ” አለችው።
እንባዋ ደረቷ ላይ ይወርዳል። ያቺ ፀዳል የመሰለች ሴት ፊቷ ድንገት
ጨለማ ለብሷል። ከመቅጽበት ዕድሜዋ ላይ ዓመታት የተጨመሩ
መስለዋል። ከዐይኗም ከአፍንጫዋም የሚወርደው ፈሳሽ አልቃሻ ሕፃን ልጅ አስመስሏታል።
ኒቆላዎስና አባ ዐደራ ተረበሹ። እናቷና አያቷ ለቅሷቸውን አቋርጠው በድንጋጤ ተመለከቷት።
“አዎ... ኸዝኸ በኋላ ምን ዓለም አለኝ? እኔም እንደ ባለቤቴ መሬት
እስትገባ ዓለሜ ምናኔ ነው። እሳቸው ሙተው እኔ እንዴት ባለም
ኖራለሁ? ልዤን ይዤ ኸዳለሁ” እያለች ጮኸች።
ኒቆላዎስ፣ “የለም የለም፤ እኼማ አይሆንም” አላት፣ ተጠግቷት።
“ደሞስ ምናኔ ማን ያደርስሻል? የጃንሆይ ጠላቶች ወይም ወህኒ
አምባ ያሉ ደጋፊዎች ምንገድ ላይ ጠብቀው አንቺንም ልዥሽንም
ይገድሏችኋል። ባይገድሏችሁ ስንኳ መውጫና መውረጃ የሌለው ወህኒ አምባ ወስደው ያስሯችኋል። ገዳም ብትገቢም ጃንሆይ ቅባት ሃይማኖት
ተከታይ ነበሩ ተብለው ስለሚጠረጠሩ እዚያ ብዙ የተዋሕዶ መነኩሴ ጠላቶች አሏቸው፤ ይጣሉሻል” አላት።
እሷ ግን፣ “በቁስቋሟ ተዉኝ! ተዉኝ” እያለች እጆቿን እያርገበገበች ተማጸነቻቸው።
ያን ጊዜ አባ ዐደራ፣ “እቴጌ መቸም መቀበል እንጂ ምን ማረግ ይቻላል? ኸሞት ሚቀር የለ። አሁን እርስዎ እንደዝኸ ሲሆኑ ሳንዘጋጅ የጃንሆይ መሞት የተሰማ እንደሁ ሁከት ይነሳል። ወህኒ ያሉትም እግረ ሙቃቸውን ፈተው ይመጣሉ። ንጉሥ ሞተ ሲባል ሚሆነውን እናውቃለን። ባክዎ ይጠንክሩልን” እያሉ ተለማመኗት።
ዮልያናም፣ “የኔ ልዥ! ባክሽ ጠንክሪ። እንደዝህ መሆን ደግ ማዶል” እያሉ እንባዋን በነጠላቸው ጠራረጉላት፣ የራሳቸውን ለመግታት
እየታገሉ።
“ልጄ በጡቴ ይዤሻለሁ! በኢያሱ ይዠሻለሁ! በምትወጃት በቁስቋም ማርያም ይዠሻለሁ! በምትወጃቸው ባባትሽ አጥንት ይሻለሁ በርቺልኝ” እያሉ እንኰዬም ሙሾ እንደሚያወርዱ ሁሉ እጃቸውን ወደ ኋላ አድርገው እንባቸውን እያዘሩ ለመኗት።
እሷ ግን እንባዋን መግታት አቃታት፤ አልጽናና አለች።
ኒቆላዎስ አንዴ እንድታዳምጠው ለምኗት የንጉሠ ነገሥቱን ኑዛዜ
ቃል በቃል ነገራት።
“ምን እንደተሰማቸው አላወቅሁም ብቻ እኔን አስጠሩኝ። ኒቆላዎስ...
ዐደራ ምልህ ልዤን... አሉኝ፣ ድምጣቸው እየተቆራረጠ። ልዤን
ኢያሱን እንድታነግሥልኝ። ለነገሥታት ሚደረገውን ሥርዐት ሁሉ... ቅባዓ ንጉሡንም ዘውዱንም... አርገህ እንዲነግሥልኝ። እናቱ ምንትዋብ
ብልህ ናት ትርዳው፤ ኸጎኑ ትሁን። እሷ አገር መምራትና... ማስተዳደር
ትችላለች። አርቆ አስተዋይና እዝጊሃር የባረካት ሰው ናት። አገሬን... አገሬን ኸልዣችን ጋር ሁና፣ ተባህር እስተ ባህር ታስተዳድር። አገሬ.. ምንም ዓይነት በደል እንዳይፈጠምባት። እኔ የዠመርሁትን ሁሉ. አጠናክረሽ ቀጥይ፤ በዐጸደ ነፍስ ኹኜም አልለይሽም በልልኝ። ሁላችሁም ቃሌን ንገሩልኝ…. ዐደራ” ብለው አንቺን እንድንጠራላቸው
ሲጠይቁ፤ ደም ባፍ ባፍንጫቸው ያለማቋረጥ ወረደ። ግዝየም አላገኙ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች።”
ምንትዋብ፣ ተናግሮ ሲጨርስ ሳግ እየተናነቃት ጣሪያውን፣
ግድግዳውን፣ ወለሉን፣ ሁሉንም በየተራ ተመለከተች። እነሱ ምን
እያሰበች እንደሆነ መገመት አቃታቸው። አንዴ እርስ በእርስ እየተያዩ ሌላ ጊዜ እሷን እያዩ ከአፉ የሚወጣውን ለመስማት ተጠባበቁ።
👍11❤1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ፣ ኢያሱ ራቱን እስኪበላና እስኪተኛ ጠብቃ እሷም በድንጋጤና በለቅሶ የደነዘዘ ሰውነቷን ለማሳረፍ ከጎኑ ጋደም አለች። አካሏ ዝሎ፣ መንፈሷ ረግቦ፣ እንቅልፍ በዐይኗ አልዞር አለ። አእምሮዋ በውስጡ ያለተራ ብቅ ጭልጥ የሚለውን የሐሳብ ውዥንብር መቆጣጠር ተሳነው። መላ የጠፋው አእምሮዋ ቢሰክንልኝ ብላ ከመኝታ ክፍሏ ወደ ሰገነቱ ከሚያወጡት ከሶስቱ በሮች በመካከለኛው በኩል አድርጋ ሰገነቱ ላይ ቆመች። ባሏም ብዙ ጊዜ በዛ በር እየወጡ፣ አንዳንዴም አብረው እየሆኑ ከተማውንና ግቢውን ይቃኙ ነበርና እንባ ተናነቃት።
ለሰባት ዓመታት ያህል ከእሳቸው ጋር ያሳለፈችውን ሕይወት
በሐሳቧ መለስ ብላ አየች። ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተራ ሰው እናት አባቷ
ቤት መደብ ላይ ተኝተው ያስታመመቻቸውን አስታወሰች። ምንትዋብ ብለው ስም ያወጡላት፣ “የኔ ዓለም” እያሉ ያቆላመጧት ሁሉ በየተራ ፊቷ ድቅን አሉባት። ምነው እንዲህ ዕድሜያቸውን አሳጠረባቸው?
አለችና ምርር ብላ አለቀሰች።
ከቤተመንግሥት ግቢ አሻግራ ጥቅጥቅ ባለው ጭለማ ውስጥ ጐንደርን ለማየት ሞከረች። ማታ ማታ ጐንደርን ያለ ከልካይ ከሚፈትሹት ጅቦች ሌላ የሚንቀሳቀስ ነገር የለም። አልፎ አልፎ ጅቦቹን ከሚያስፈራሩት
ውሾች ጩኸት በስተቀር ድምፅም አይሰማም።
ምንትዋብ ከጐንደር ወደ ራሷ ተመለሰች። ሕይወት ያልታሰበ
ፀጋ አምጥታላት መልሳ መንጠቋ ገረማት። የሕይወት መንገዶች
አለመጣጣማቸው ደነቃት። ሞት ሌላው የሕይወት ገፅታ መሆኑን
አሰበች። ሕይወት ምስጢሯን ያካፈለቻት መስሎ ተሰማት። ነገ እዛ ራሷ ረጋፊ መሆኗ በአእምሮዋ ተመላለሰና ዘገነናት። ለጊዜውም ቢሆን የመኖር ትርጉሙ ተናጋባት። የሙት ሚስት መሆኗ ወለል ብሎ
ታያት። ሞት ተስፋዋን ሁሉ ሸራረፈባት።
በዚያች ቅጽበት ሕይወቷ ዳግመኛ እንደተለወጠ ተረዳች።
መኝታ ክፍላቸው ስትገባ እንደገና እንባ አሸነፋት። ቤቱ የሚበላት፣
አልጋው ብቻዋን በመምጣቷ የሚታዘባት መሰላት። ለባሏ እንደሚገባቸው ያላዘነች፣ ያላነባች መስሎ ተሰማት። ቆም ብላ ክፍሉን ቃኘች። በርካታ
ትዝታዎች በአእምሮዋ ውስጥ ተመላለሱ። ወደ ኢያሱ ስትመለከት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ነው። ሆዷ ባባ። አባቱን ሲሰናበታቸው ምን ተሰምቶት እንደሆነ መገመት አቃታት። እመንናለሁ ብላ የእሱን ሕይወት አደጋ ልትጥል እንደነበር አስታወሰችና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ተጠግታው ራሱን እያሻሸች፣ በዚች ምድር ላይ ካሉ ክፉ ነገሮች ሁሉ፣ከሞት ጭምር፣ ልትደብቀው እቅፏ ውስጥ ሽጉጥ አድርጋው ጋደም
አለች።
አእምሮዋ እረፍት አጥቶ እንቅልፍ በዐይኗ ሳይዞር ወፍ ተንጫጫ።
ተነስታ ወደ ሰገነቱ ወጣች። ሰማይና ምድር ገና አልተላቀቁም።
ጐንደርም ገና እንቅልፍ ላይ ናት። በቦዘዙ ዐይኖቿ ዙርያውን አየች።
የጠዋቱ ቅዝቃዜ ፊቷን ሲዳስሳት፣ ነቃ አለች።
አሻግራ ጐንደርን ወደከበቧት ተራሮች ተመለከተች። ፍም እሳት
የከበባት የምትመስለውን ፀሐይ ብቅ ስትል ስታይ የጥድፊያ ስሜት
ተሰማት። በመመርያ ኸዋና ዋናዎቹ ግቢ አዛዥና ኸሊጋባው፣
እንዲሁም ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክራለሁ። ጃንሆይ አገር አለ ምክር፣ ቤት አለ ማገር ይሉ ማልነበር? ኸዛ በኋላ፣ ኢያሱ በምሥጢር ይነግሣል። የልጄቼን አልጋማ ለማንም አሳልፌ አልሰጥም
ለካንስ እሷም መንገሷ ነው! ደነገጠች።
ይህ ሳይታሰብ እላይዋ ላይ የወደቀው ኃላፊነት ከየት እንደመጣ ማወቅ አቃታት። ሃገር ልታስተዳድር መሆኑ ሲገባት ታላቅ የኃላፊነት ስሜት ተጫጫናት፡፡ እሳቸው ያሰቡትን ሁሉ ሳያሳኩ አለፉ፤ እኔስ ብሆን መቸ እንደምሞት በምን አውቃለሁ? ሞት እንደሁ ለማንም አይመለስ፡ ብቻ እንዳው አንዴ የሳቸውን ቀብርና የልጄን ንግሥ
ያለምንም ሳንካ ላሳካ እያለች አእምሮዋ ውስጥ የሚወራጨውን ሐሳብ ሁሉ በየፈርጁ ማስቀመጥ ሞከረች።
ድንገት ክፉኛ የመንገሥ ፍላጎት አደረባት። ባሏ፣ “እሷ አገር
ማስተዳደር ትችላለች” ያሉት በከንቱ እንዳልሆነ፣
ስለቤተመንግሥትም ጉዳይ ቢሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት በቂ
እውቀት እንዳካበተች፣ በደጉ ጊዜ ቤተመንግሥት ውስጥ ቦታቸውን
ያመቻቸችላቸው የኒቆላዎስ፣ የወልደልዑል፣ የአርከሌድስና
የሌሎቹም መኖር ታላቅ ድጋፍ እንደሚሆናት ተረዳች። ኒቆላዎስ
እያረጀ በመምጣቱ፣ ወንድሟ ወልደልዑል ጉልህ ችሎታ በማሳየቱና ቤተመንግሥት ውስጥ የማይናቅ አስተዋጽኦም በማድረጉ ቀኝ እጇ ሊሆን እንደሚችል አመነች። ዐዲስ ማንነት ውስጧ ሲጠነሰስ ተሰማት።
ከፍተኛውን የሥልጣን ዕርከን ስትወጣ ታያት።
ልቧ መታ፤ መላ ሰውነቷ ተቅበጠበጠ። ዳግም የጥድፊያ ስሜት ተሰማት። ይህንን ዕድል ለማንም አሳልፋ ልትሰጥ እንደማትችልና የኢያሱን ሆነ የራሷን ንግሥ ለማስከበር በችሎታዋና ሥልጣንዋ ስር ያለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለባት ለራሷ አስገነዘበች። አሁን ፊቷ ተደቅኖ
የሚታያት ምኞት ወይንም ተስፋ ሳይሆን በቅርብ ያለ፣ሊጨበጥ የሚችል በመሆኑና ከለቀቀችው፣ ካመነታች እዳው ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለልጇ ጭምር በመሆኑ በአስቸኳይ እርምጃ መውሰድ
እንዳለባት ተረዳች።
እኔም ኢያሱም ኸነገሥን በኋላ፣ ኣመጥ እንዳይኖር ጥርጣሬ
አስወግጀ ሰዉ እኔ ላይ አመኔታ እንዲኖረው ማረግ አለብኝ። መቸም መልካም ሥራ ኸሠራሁና ጥሩ አርጌ ኻስተዳደርሁ ሰዉ ይደግፈኛል::እምነትም ይጥልብኛል አለች፣ ሞላ ባለ ልብ። ከሁን ታሪክ የምትሠራበት፣ ስሟን ካለፉት ነገሥታት ተርታ የምታሰልፍበት ወቅት
እንደተቃረበ አስተዋለች። ሃገሯ ታላቅ ጥንካሬ፣ ዘዴ፣ ቆራጥነትና
ቀናነት እንደምትጠብቅባት ተረዳች።
ከሐሳቧ ስትነቃ ምድር ለቋል፤ ጐንደር ብርሃን ለብሳለች፤ ነፍስ
ዘርታለች። ። ጐንደርን ለመጀመሪያ ጊዜ በተለየ ዐይን አየቻት። ጐንደር
ጐንደር! አለች፣ በለሆሳስ፡ ፊቷን እያዟዟረች ከተማዋን የከበቡትን
ሰንሰለታማ ተራራዎች ትክ ብላ አየቻቸው። በተፈጥሮዋ የጠላት
መከላከያ አላት አለች። እንደገና ከተማዋን ከላይ ወደታች ቃኘች።
ጐንደር... ያቺ የነገሥታቱ፣ የመሣፍንቱና የመኳንንቱ የትንቅንቅ ቦታ ሳትሆን የተለየች ጐንደር ሆና፣ እንባዋን ጠራርጋ ወጣ ገባ ስትል ታየቻት። የዕድል ማሳ ሆና እሷ ማሳው ላይ ስትዘራ ጐንደር ስታብብ፣ስታፈራ፣ ይበልጥ ገናና ስትሆን ታያት።
በራሷ አምሳል የቀረጸቻት ጐንደር ፊቷ ወለል አለች።
ጐንደርን በጃን ተከል በኩል ለማየት ወደ ላይኛው ሰገነት በደረጃ ወጣች። የሁሉ መኖሪያ፣ ሁሉን እንደ ሃይማኖቱ፣ እንደ ሙያውና እንደ ልማዱ የምታስተናግደውንና፣ መንፈሰ ለጋሷን ጐንደርን እንደ
ዐዲስ ወደደቻት፤ ከክፉ ልትታደጋት ፈቀደች። ምን ዓይነት ቦታ እንደሆነችና ሕዝቧም ምን ዓይነት እንደሆነ ይበልጥ ማወቅ ፈለገች።
ልክ በዛን ሰዐት የእሷም የጐንደርም ዕጣ የተለየ አቅጣጫ ያዘ።
እንዴ! አገሬ? አገሬስ? ጐንደር አላገር ትኖራለች እንዴ? አለች
ደረቷን እየመታች። አገሬ ውስጥ ሰላም አምጥቸ እኼ ነው ምኞቴ
አለች፣ ባሏ የነበረባቸውን ዓመጽ አስባ። ሃገሯን ልትታደጋት፣
ልታረጋጋት፣ ሰላም ልታሰፍንባት ወሰነች።
የደብረብርሃን ሥላሤ ደወል ሲደወል ከሐሳቧ ነቃች፣ ተረበሸች።
ደወሉ ለአባታቸው ለአፄ አድያም ሰገድ ኢያሱ ከሆላንድ ንጉሥ
የተላከ ነበርና ንጉሠ ነገሥቱ ደወሉን ሲሰሙ ከእንቅልፋቸው ብንን ብለው ሲያማትቡ፣ ተነሥተው ዳዊታቸውንና ውዳሴ ማርያማቸውን ሲደግሙ ፊቷ ላይ ድቅን አለ። አየ ያ ሁሉ ቀረ አለችና እንባዋን ጠራረገች።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ፣ ኢያሱ ራቱን እስኪበላና እስኪተኛ ጠብቃ እሷም በድንጋጤና በለቅሶ የደነዘዘ ሰውነቷን ለማሳረፍ ከጎኑ ጋደም አለች። አካሏ ዝሎ፣ መንፈሷ ረግቦ፣ እንቅልፍ በዐይኗ አልዞር አለ። አእምሮዋ በውስጡ ያለተራ ብቅ ጭልጥ የሚለውን የሐሳብ ውዥንብር መቆጣጠር ተሳነው። መላ የጠፋው አእምሮዋ ቢሰክንልኝ ብላ ከመኝታ ክፍሏ ወደ ሰገነቱ ከሚያወጡት ከሶስቱ በሮች በመካከለኛው በኩል አድርጋ ሰገነቱ ላይ ቆመች። ባሏም ብዙ ጊዜ በዛ በር እየወጡ፣ አንዳንዴም አብረው እየሆኑ ከተማውንና ግቢውን ይቃኙ ነበርና እንባ ተናነቃት።
ለሰባት ዓመታት ያህል ከእሳቸው ጋር ያሳለፈችውን ሕይወት
በሐሳቧ መለስ ብላ አየች። ንጉሠ ነገሥቱ እንደ ተራ ሰው እናት አባቷ
ቤት መደብ ላይ ተኝተው ያስታመመቻቸውን አስታወሰች። ምንትዋብ ብለው ስም ያወጡላት፣ “የኔ ዓለም” እያሉ ያቆላመጧት ሁሉ በየተራ ፊቷ ድቅን አሉባት። ምነው እንዲህ ዕድሜያቸውን አሳጠረባቸው?
አለችና ምርር ብላ አለቀሰች።
ከቤተመንግሥት ግቢ አሻግራ ጥቅጥቅ ባለው ጭለማ ውስጥ ጐንደርን ለማየት ሞከረች። ማታ ማታ ጐንደርን ያለ ከልካይ ከሚፈትሹት ጅቦች ሌላ የሚንቀሳቀስ ነገር የለም። አልፎ አልፎ ጅቦቹን ከሚያስፈራሩት
ውሾች ጩኸት በስተቀር ድምፅም አይሰማም።
ምንትዋብ ከጐንደር ወደ ራሷ ተመለሰች። ሕይወት ያልታሰበ
ፀጋ አምጥታላት መልሳ መንጠቋ ገረማት። የሕይወት መንገዶች
አለመጣጣማቸው ደነቃት። ሞት ሌላው የሕይወት ገፅታ መሆኑን
አሰበች። ሕይወት ምስጢሯን ያካፈለቻት መስሎ ተሰማት። ነገ እዛ ራሷ ረጋፊ መሆኗ በአእምሮዋ ተመላለሰና ዘገነናት። ለጊዜውም ቢሆን የመኖር ትርጉሙ ተናጋባት። የሙት ሚስት መሆኗ ወለል ብሎ
ታያት። ሞት ተስፋዋን ሁሉ ሸራረፈባት።
በዚያች ቅጽበት ሕይወቷ ዳግመኛ እንደተለወጠ ተረዳች።
መኝታ ክፍላቸው ስትገባ እንደገና እንባ አሸነፋት። ቤቱ የሚበላት፣
አልጋው ብቻዋን በመምጣቷ የሚታዘባት መሰላት። ለባሏ እንደሚገባቸው ያላዘነች፣ ያላነባች መስሎ ተሰማት። ቆም ብላ ክፍሉን ቃኘች። በርካታ
ትዝታዎች በአእምሮዋ ውስጥ ተመላለሱ። ወደ ኢያሱ ስትመለከት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ነው። ሆዷ ባባ። አባቱን ሲሰናበታቸው ምን ተሰምቶት እንደሆነ መገመት አቃታት። እመንናለሁ ብላ የእሱን ሕይወት አደጋ ልትጥል እንደነበር አስታወሰችና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ተጠግታው ራሱን እያሻሸች፣ በዚች ምድር ላይ ካሉ ክፉ ነገሮች ሁሉ፣ከሞት ጭምር፣ ልትደብቀው እቅፏ ውስጥ ሽጉጥ አድርጋው ጋደም
አለች።
አእምሮዋ እረፍት አጥቶ እንቅልፍ በዐይኗ ሳይዞር ወፍ ተንጫጫ።
ተነስታ ወደ ሰገነቱ ወጣች። ሰማይና ምድር ገና አልተላቀቁም።
ጐንደርም ገና እንቅልፍ ላይ ናት። በቦዘዙ ዐይኖቿ ዙርያውን አየች።
የጠዋቱ ቅዝቃዜ ፊቷን ሲዳስሳት፣ ነቃ አለች።
አሻግራ ጐንደርን ወደከበቧት ተራሮች ተመለከተች። ፍም እሳት
የከበባት የምትመስለውን ፀሐይ ብቅ ስትል ስታይ የጥድፊያ ስሜት
ተሰማት። በመመርያ ኸዋና ዋናዎቹ ግቢ አዛዥና ኸሊጋባው፣
እንዲሁም ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክራለሁ። ጃንሆይ አገር አለ ምክር፣ ቤት አለ ማገር ይሉ ማልነበር? ኸዛ በኋላ፣ ኢያሱ በምሥጢር ይነግሣል። የልጄቼን አልጋማ ለማንም አሳልፌ አልሰጥም
ለካንስ እሷም መንገሷ ነው! ደነገጠች።
ይህ ሳይታሰብ እላይዋ ላይ የወደቀው ኃላፊነት ከየት እንደመጣ ማወቅ አቃታት። ሃገር ልታስተዳድር መሆኑ ሲገባት ታላቅ የኃላፊነት ስሜት ተጫጫናት፡፡ እሳቸው ያሰቡትን ሁሉ ሳያሳኩ አለፉ፤ እኔስ ብሆን መቸ እንደምሞት በምን አውቃለሁ? ሞት እንደሁ ለማንም አይመለስ፡ ብቻ እንዳው አንዴ የሳቸውን ቀብርና የልጄን ንግሥ
ያለምንም ሳንካ ላሳካ እያለች አእምሮዋ ውስጥ የሚወራጨውን ሐሳብ ሁሉ በየፈርጁ ማስቀመጥ ሞከረች።
ድንገት ክፉኛ የመንገሥ ፍላጎት አደረባት። ባሏ፣ “እሷ አገር
ማስተዳደር ትችላለች” ያሉት በከንቱ እንዳልሆነ፣
ስለቤተመንግሥትም ጉዳይ ቢሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት በቂ
እውቀት እንዳካበተች፣ በደጉ ጊዜ ቤተመንግሥት ውስጥ ቦታቸውን
ያመቻቸችላቸው የኒቆላዎስ፣ የወልደልዑል፣ የአርከሌድስና
የሌሎቹም መኖር ታላቅ ድጋፍ እንደሚሆናት ተረዳች። ኒቆላዎስ
እያረጀ በመምጣቱ፣ ወንድሟ ወልደልዑል ጉልህ ችሎታ በማሳየቱና ቤተመንግሥት ውስጥ የማይናቅ አስተዋጽኦም በማድረጉ ቀኝ እጇ ሊሆን እንደሚችል አመነች። ዐዲስ ማንነት ውስጧ ሲጠነሰስ ተሰማት።
ከፍተኛውን የሥልጣን ዕርከን ስትወጣ ታያት።
ልቧ መታ፤ መላ ሰውነቷ ተቅበጠበጠ። ዳግም የጥድፊያ ስሜት ተሰማት። ይህንን ዕድል ለማንም አሳልፋ ልትሰጥ እንደማትችልና የኢያሱን ሆነ የራሷን ንግሥ ለማስከበር በችሎታዋና ሥልጣንዋ ስር ያለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለባት ለራሷ አስገነዘበች። አሁን ፊቷ ተደቅኖ
የሚታያት ምኞት ወይንም ተስፋ ሳይሆን በቅርብ ያለ፣ሊጨበጥ የሚችል በመሆኑና ከለቀቀችው፣ ካመነታች እዳው ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለልጇ ጭምር በመሆኑ በአስቸኳይ እርምጃ መውሰድ
እንዳለባት ተረዳች።
እኔም ኢያሱም ኸነገሥን በኋላ፣ ኣመጥ እንዳይኖር ጥርጣሬ
አስወግጀ ሰዉ እኔ ላይ አመኔታ እንዲኖረው ማረግ አለብኝ። መቸም መልካም ሥራ ኸሠራሁና ጥሩ አርጌ ኻስተዳደርሁ ሰዉ ይደግፈኛል::እምነትም ይጥልብኛል አለች፣ ሞላ ባለ ልብ። ከሁን ታሪክ የምትሠራበት፣ ስሟን ካለፉት ነገሥታት ተርታ የምታሰልፍበት ወቅት
እንደተቃረበ አስተዋለች። ሃገሯ ታላቅ ጥንካሬ፣ ዘዴ፣ ቆራጥነትና
ቀናነት እንደምትጠብቅባት ተረዳች።
ከሐሳቧ ስትነቃ ምድር ለቋል፤ ጐንደር ብርሃን ለብሳለች፤ ነፍስ
ዘርታለች። ። ጐንደርን ለመጀመሪያ ጊዜ በተለየ ዐይን አየቻት። ጐንደር
ጐንደር! አለች፣ በለሆሳስ፡ ፊቷን እያዟዟረች ከተማዋን የከበቡትን
ሰንሰለታማ ተራራዎች ትክ ብላ አየቻቸው። በተፈጥሮዋ የጠላት
መከላከያ አላት አለች። እንደገና ከተማዋን ከላይ ወደታች ቃኘች።
ጐንደር... ያቺ የነገሥታቱ፣ የመሣፍንቱና የመኳንንቱ የትንቅንቅ ቦታ ሳትሆን የተለየች ጐንደር ሆና፣ እንባዋን ጠራርጋ ወጣ ገባ ስትል ታየቻት። የዕድል ማሳ ሆና እሷ ማሳው ላይ ስትዘራ ጐንደር ስታብብ፣ስታፈራ፣ ይበልጥ ገናና ስትሆን ታያት።
በራሷ አምሳል የቀረጸቻት ጐንደር ፊቷ ወለል አለች።
ጐንደርን በጃን ተከል በኩል ለማየት ወደ ላይኛው ሰገነት በደረጃ ወጣች። የሁሉ መኖሪያ፣ ሁሉን እንደ ሃይማኖቱ፣ እንደ ሙያውና እንደ ልማዱ የምታስተናግደውንና፣ መንፈሰ ለጋሷን ጐንደርን እንደ
ዐዲስ ወደደቻት፤ ከክፉ ልትታደጋት ፈቀደች። ምን ዓይነት ቦታ እንደሆነችና ሕዝቧም ምን ዓይነት እንደሆነ ይበልጥ ማወቅ ፈለገች።
ልክ በዛን ሰዐት የእሷም የጐንደርም ዕጣ የተለየ አቅጣጫ ያዘ።
እንዴ! አገሬ? አገሬስ? ጐንደር አላገር ትኖራለች እንዴ? አለች
ደረቷን እየመታች። አገሬ ውስጥ ሰላም አምጥቸ እኼ ነው ምኞቴ
አለች፣ ባሏ የነበረባቸውን ዓመጽ አስባ። ሃገሯን ልትታደጋት፣
ልታረጋጋት፣ ሰላም ልታሰፍንባት ወሰነች።
የደብረብርሃን ሥላሤ ደወል ሲደወል ከሐሳቧ ነቃች፣ ተረበሸች።
ደወሉ ለአባታቸው ለአፄ አድያም ሰገድ ኢያሱ ከሆላንድ ንጉሥ
የተላከ ነበርና ንጉሠ ነገሥቱ ደወሉን ሲሰሙ ከእንቅልፋቸው ብንን ብለው ሲያማትቡ፣ ተነሥተው ዳዊታቸውንና ውዳሴ ማርያማቸውን ሲደግሙ ፊቷ ላይ ድቅን አለ። አየ ያ ሁሉ ቀረ አለችና እንባዋን ጠራረገች።
👍13❤2
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
.....ጐንደርን እንዴት አርጌ ኑሯል ጥዬ ለመኸድ፣ ጭራሹንም ልመንን አስቤ የነበረው? አገሬንስ ለማን ጥየ ነበር ገዳም ልገባ ያሰብሁት? አልኸድም፣ አገሬን እታደጋታለሁ አለች።
ምን ያህል እዚያ እንደቆመች አላወቀችም። ፀሐይዋን ስታያት ሞቅ ብላለች። እስቲ ለዝኸ ከባድ ቀን ልዘገጃጅ ብላ ወደታች ወረደች።
ተዘጋጅታ ስትጨርስ፣ ቤተሰቧን አስከትላ ወደ አሸዋ ግንብ ሄደች።
የተጠሩት መሣፍንት፣ መኳንንት፣ አቡኑ፣ ዕጨጌውና ዐቃቤ ሰዐቱ
ሲገቡ የተጠሩበትን ምክንያት መገመት አልቻሉም። እሷ ምንም
እንዳልተፈጠረ ተረጋግታ ተቀምጣለች። እነሱ ንጉሠ ነገሥቱ ከአሁን አሁን ይመጣሉ በማለት በር በሩን ይመለከታሉ። በመጨረሻም ግራዝማች ኒቆላዎስ ከተቀመጠበት ተነሥቶ በመሃከላቸው ሲቆም ፀጥታ ሰፈነ። የሁሉ ዐይን ወደ እሱ ሆነ። ቀደም ብሎ ምንትዋብ
የነገረችውን መልዕክት አስተላለፈ።
ክቡራን ሆይ! ለእናንተ ሚደርስ መልክት ኸጃንሆይ ይዠ እናንተ
ዘንድ ቀርቤአለሁ። ልዤን ኢያሱን አንግሡልኝ፤ ይቀመጥ በወንበሬ፣
ይናገር በከንፈሬ፣ ይፍረድ - ይዳኝ ላገሬ። እኔ መንኩሻለሁ፤ ገዳም
ኸጃለሁ። አልመለስም። ሁሉንም ነገር እንደሚገባ አርጉ” ብለዋል
አላቸው።
ያልታሰበ ዜና በመሆኑ ሁሉም ተደናገጡ። ንጉሠ ነገሥቱ የሞቱ
የመሰላቸውም አልጠፉ። ያንን የሚያመላክት ነገር ግን ባለማየታቸው ግራ ተጋቡ። በእውነትም መንኩሰው ይሆናል ብለው ያመኑት የንጉሠ ነገሥቱን ጥልቅ ሃይማኖተኝነት ስለሚያውቁ ለማመን ብዙም አልተቸገሩ። አባታቸው ታላቁ ኢያሱ እንደዚሁ በመጨረሻ ዘመነ ንግሥናቸው፣ “እስተ መቸ ድረስ በሥጋዊ ባሕር ጠልቄ፣ ተጨንቄ ኖራለሁ” ብለው ጣና ገዳም ገብተው ስለነበር፣ ልጅየውም የአባታቸውን
ፈለግ መከተላቸው እምብዛም የሚያጠራጥር አልሆነባቸውም።
ባንድ ቃል፣ “ይበጅ! ይበጅ! ግድ የለም፤ እኼ ፈቃደ እዝጊሃር ነው”
ብለው ተበተኑ።
ምንትዋብ ብላቴን ጌታ ዳዊትና ሻለቃ ወረኛን ከሙስሊም
ነፍጠኞችና ከፎገራ የዘዌና የቱለማ መሪዎች ጋር በመሆን በፍጥነት ሄደው ወህኒ አምባን በጥብቅ እንዲጠብቁ ትዕዛዝ ሰጠች፤ መሣሪያም
እንዲሰጣቸው አዘዘች።
ለኒቆላዎስ፣ “ከካህናቱም ኢያሱን ቀብተው እንዲያነግሡ ሊቁን
ጽራግ ማሰሬ ማሞን፣ ቄስ እልፍዮስንና ሁለቱን ጸሐፍተ ትዕዛዝ...” እያለች የንግሥ ሥርዐት የሚፈጽሙትንና ሌሎች መገኘት አለባቸው ብላ ያሰበቻቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ሰጠችው። ግራዝማች ኒቆላዎስ መልዕክቱን እጅ ነስቶ ተቀበለ።
ሐሙስ ሌሊት ግራዝማች ኒቆላዎስ፣ አፈ ንጉሥ ኢዮብና አዛዥ ባለሟሎች ዐይን ለመሸሸግ ሻሸና በተባለው የስርቆሽ መንገድ የንግሥ አርከሌድስ ምንትዋብን፣ ኢያሱን፣ ዮልያናንና እንኰዬን ከቤተመንግሥት ሥርዐት ወደሚፈፀምበት ወደ መናገሻ ግንብ ወሰዷቸው። መናገሻ ውስጥ በአፄ በካፋ ጽራግ ማሰሬነት ማዕረግ የተሾሙትንና ቤተመንግሥት ተቀማጭ የሆኑትን ንጉሥ አንጋሹ መነኩሴ ማሞ፣ ቡራኬ ሰጪው
ቄስ እልፍዮስ፣ የመናገሻ ግንብ አጋፋሪዎች አቡሊዲስ፣ ገላውዲዎስ፣ አደሩና ሌሎችም ባሉበት ምንትዋብ ዙፋን ላይ ስትቀመጥ ኢያሱ እግሯ ሥር ተቀመጠ። ኢያሱ ነገሩ እምብዛም ባይገባውም አባቱ እንደሞቱና ሊነግሥ መሆኑ ስለተነገረው የንግሥናው ደስታ ሳይሆን
የአባቱ ሞት ሐዘን ፊቱ ላይ ይታያል።
የንግሥ ሥርዐቱን ለመጀመር በጅሮንድ አብርሃም ዘውዱን ለጽራግ ማሰሬ ማሞ አቀረቡ። ጽራግ ማሰሬ ማሞም ዘውዱን አፄ በካፋ ዙፋን ላይ አስቀመጡ። ንጉሥ ሲነግሥ የሚጸለየውን ጸሎት ጸለዩ።ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከብሉያትና ከሐዲስ ኪዳንም የተመረጡ ምንባቦችን አነበቡ። አቡነ ዘበሰማያትም ደገሙ። ኢያሱን ወደ እሳቸው አምጥተው
እጃቸውን አናቱ ላይ አስቀምጠው በአንብሮተ እድ ባረኩት፣ ጸለዩለት፡-
“አቤቱ ፍርድህን ለንጉሡ ስጠው
እውነትኸንም ለንጉሡ ልጅ
ሕዝብኸን በእውነት ይፈርድላቸው ዘንድ
ድኾችኸንም በፍትሕ ይገዛ ዘንድ
አድባር አውጋሩ የሕዝብኸን ሰላም ይቀበሉ።
ከዚያም መከሩት፣
ኰንን በጽድቅ ነዳያነ ሕዝበከ
ወአድኅኖሙ ለደቂቀ ምስኪናኒከ
ወአሕስሮ ለዕቡይ
ተስፋም ሰጡት፡-
በዘመኑ እውነት ይሠርጻል
ከባሕር እስከ ባሕርም ይገዛል
ከወንዞችም እስከ ዓለም ጥጋጥግ
ኢትዮጵያ ይገዙለታል
ጠላቶቹ ግን አፈር ይበላሉ።”
ከዚህና ከበርካታ ሌሎች ጸሎቶች በኋላ፣ በዕንቁ ያጌጠውን የአባቱን
ዘውድ ራሱ ላይ ደፉለት፣ በአባቱ ዙፋንም ላይ አስቀመጡት። ከዚያም የጫነው ዘውድ ለጌጥ የተሠራ ሳይሆን የሕዝቡን ችግርና መከራ የሚሸከምላቸው መሆኑን የሚዘክር፣ ንጉሣቸውና አገልጋያቸው መሆኑን
የሚያሳስብ እንደሆነ ተናግረው መረቁት፡ አስመረቁት፡-
“ሺሕ ዓመት ንገሥ
ወንድ ልጅ ለፈረስ፣ ሴት ልጅ ለበርኖስ አድርስ።”
አሉት፤ በዚያው የተሰበሰው ሕዝብም ይህንን ሦስት ጊዜ መላልሰው በአንድ ድምጽ አስተጋቡ።
“ዳዊት ቤት ቀርነ መድኃኒት የሆነ ንጉሥ ስላነሳልን እግዚአብሔር
ይመስገን፤” አሉ፣ ጽራግ ማሰሬ ማሞ።
ኢያሱ ዳግማዊ ኢያሱ ንጉሠ ነገሥት ተብሎ ነገሠ።
ጽራግ ማሰሬ ማሞ ዙፋኑ ስር ተንበርክከው ሰገዱለት። በዓሉ ላይ ተገኝቶ የነበረው ሁሉ ተነስቶ ለሰባት ዓመቱ ልጅ ለኢያሱ ሰገደ።
በተራው ንጉሥ ባራኪው እልፍዮስ ወደ ኢያሱ ተጠግተው የብዙ
ታላላቅ ነገሥታት ነብያትና ታላላቅ ነገስታት በረከት እንዲያድርበት መረቁት።
“የቅዱስ ዳዊት በረከት ይደርብህ። የጠቢቡ ሰለሞን ፍትሕና ጥበብ አይለይህ። የኢዮሲያስ፣ የሕዝቅያስና የቆስጠንጢኖስ በረከት ይደርብህ”እያሉ ባረኩት። በመጨረሻም ለኢያሱ ዳግመኛ ሰግደው ወደነበሩበት ተመለሱ። ዘውዱ ለትንሹ ኢያሱ ከባድ በመሆኑ ጽራግ ማሰሬ ማሞ
ከራሱ ላይ አንስተውለት በክብር ጠረጴዛው ላይ አኖሩት::
ምንትዋብ ከተቀመጠችበት ተነስታ እጆቿን ዘርግታ፣ “እኔን
ታናሺቱን ለዝኸ ክብር ላበቃኝ እዝጊሃር ምስጋና ይግባው። ፈጣሪዬ ሆይ ለኔ ለባርያህ በንጉሡ በአባቱ በአጤ በካፋ ዙፋን ላይ መቀመጥ ዘር
ስለሰጠኸኝ ክብር ምስጋና ይግባህ” ብላ ምስጋና አቀረበች። በኋላም ኢያሱን ላነገሠው ለጽራግ ማሰሬ ማሞ፣ ለአንጋሽ እንደሚደረገው አስር ሰቅለ ወርቅ እንዲሰጥ ትዕዛዝ አስተላለፈች።
ትውፊቱን ጥሳ፣ የልጇ ንግሥ ላይ ባሏን ያነገሡት አቡነ ክርስቶዶሌ
ተገኝተው ዘውድ እንዲጭኑለት እንኳን ሳታደርግ፣ መፈጸም ያለባቸውን ዋና ዋና ጉዳዮች ብቻ ፈጽማ የኢያሱ የንግሥ ሥርዐት በምሥጢር ያለአንዳች ኮሽታ ተጠናቀቀ።
ወዲያው ባሻ ኤልያስን አስጠርታ፣ ሲነጋ የንጉሠ ነገሥቱ ሕልፈትና
የኢያሱ መንገሥ እንዲታወጅና ለንጉሥ ቀብር የሚደረገውን ሥርዐት ሁሉ እንዲያደርግ አዘዘችው። እጅ ነስቶ ሄደ።
ጠዋት ላይ፣ በታዘዙት መሠረት እነባሻ ኤልያስ ድብ አንበሳ ይዘው
ወደ ጃን ተከል ወረዱ። ሊጋባው፣ ከአዛዡ በተቀበለው ትዕዛዝ መሠረት ነጋሪት እየጎሰመ፣ “አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ! የሞትንም እኛ፣ ያለንም እኛ ንጉሥ በካፋ ዐርፈዋል። ልጃቸው ኢያሱ ነግሠዋል፣ የሰማ ላልሰማ
ያሰማ። ጠላቶቻችን ይፈሩ፤ ወዳጆቻችን ትፍሥሕት ያድርጉ፣ ባለህበት እርጋ፤ ነጋዴም ነግድ፤ ገበሬም እረስ!” እያለ አዋጅ ነገረ።
ጐንደሬዎች ግልብጥ ብለው ወጡ። “ይበጅ! ይበጅ! ያድርግ!”
አሉ። በኢያሱ መንገሥ ተደሰቱ፤ እምብዛም ባይወዷቸውም ለበካፋም አለቀሱ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
.....ጐንደርን እንዴት አርጌ ኑሯል ጥዬ ለመኸድ፣ ጭራሹንም ልመንን አስቤ የነበረው? አገሬንስ ለማን ጥየ ነበር ገዳም ልገባ ያሰብሁት? አልኸድም፣ አገሬን እታደጋታለሁ አለች።
ምን ያህል እዚያ እንደቆመች አላወቀችም። ፀሐይዋን ስታያት ሞቅ ብላለች። እስቲ ለዝኸ ከባድ ቀን ልዘገጃጅ ብላ ወደታች ወረደች።
ተዘጋጅታ ስትጨርስ፣ ቤተሰቧን አስከትላ ወደ አሸዋ ግንብ ሄደች።
የተጠሩት መሣፍንት፣ መኳንንት፣ አቡኑ፣ ዕጨጌውና ዐቃቤ ሰዐቱ
ሲገቡ የተጠሩበትን ምክንያት መገመት አልቻሉም። እሷ ምንም
እንዳልተፈጠረ ተረጋግታ ተቀምጣለች። እነሱ ንጉሠ ነገሥቱ ከአሁን አሁን ይመጣሉ በማለት በር በሩን ይመለከታሉ። በመጨረሻም ግራዝማች ኒቆላዎስ ከተቀመጠበት ተነሥቶ በመሃከላቸው ሲቆም ፀጥታ ሰፈነ። የሁሉ ዐይን ወደ እሱ ሆነ። ቀደም ብሎ ምንትዋብ
የነገረችውን መልዕክት አስተላለፈ።
ክቡራን ሆይ! ለእናንተ ሚደርስ መልክት ኸጃንሆይ ይዠ እናንተ
ዘንድ ቀርቤአለሁ። ልዤን ኢያሱን አንግሡልኝ፤ ይቀመጥ በወንበሬ፣
ይናገር በከንፈሬ፣ ይፍረድ - ይዳኝ ላገሬ። እኔ መንኩሻለሁ፤ ገዳም
ኸጃለሁ። አልመለስም። ሁሉንም ነገር እንደሚገባ አርጉ” ብለዋል
አላቸው።
ያልታሰበ ዜና በመሆኑ ሁሉም ተደናገጡ። ንጉሠ ነገሥቱ የሞቱ
የመሰላቸውም አልጠፉ። ያንን የሚያመላክት ነገር ግን ባለማየታቸው ግራ ተጋቡ። በእውነትም መንኩሰው ይሆናል ብለው ያመኑት የንጉሠ ነገሥቱን ጥልቅ ሃይማኖተኝነት ስለሚያውቁ ለማመን ብዙም አልተቸገሩ። አባታቸው ታላቁ ኢያሱ እንደዚሁ በመጨረሻ ዘመነ ንግሥናቸው፣ “እስተ መቸ ድረስ በሥጋዊ ባሕር ጠልቄ፣ ተጨንቄ ኖራለሁ” ብለው ጣና ገዳም ገብተው ስለነበር፣ ልጅየውም የአባታቸውን
ፈለግ መከተላቸው እምብዛም የሚያጠራጥር አልሆነባቸውም።
ባንድ ቃል፣ “ይበጅ! ይበጅ! ግድ የለም፤ እኼ ፈቃደ እዝጊሃር ነው”
ብለው ተበተኑ።
ምንትዋብ ብላቴን ጌታ ዳዊትና ሻለቃ ወረኛን ከሙስሊም
ነፍጠኞችና ከፎገራ የዘዌና የቱለማ መሪዎች ጋር በመሆን በፍጥነት ሄደው ወህኒ አምባን በጥብቅ እንዲጠብቁ ትዕዛዝ ሰጠች፤ መሣሪያም
እንዲሰጣቸው አዘዘች።
ለኒቆላዎስ፣ “ከካህናቱም ኢያሱን ቀብተው እንዲያነግሡ ሊቁን
ጽራግ ማሰሬ ማሞን፣ ቄስ እልፍዮስንና ሁለቱን ጸሐፍተ ትዕዛዝ...” እያለች የንግሥ ሥርዐት የሚፈጽሙትንና ሌሎች መገኘት አለባቸው ብላ ያሰበቻቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ሰጠችው። ግራዝማች ኒቆላዎስ መልዕክቱን እጅ ነስቶ ተቀበለ።
ሐሙስ ሌሊት ግራዝማች ኒቆላዎስ፣ አፈ ንጉሥ ኢዮብና አዛዥ ባለሟሎች ዐይን ለመሸሸግ ሻሸና በተባለው የስርቆሽ መንገድ የንግሥ አርከሌድስ ምንትዋብን፣ ኢያሱን፣ ዮልያናንና እንኰዬን ከቤተመንግሥት ሥርዐት ወደሚፈፀምበት ወደ መናገሻ ግንብ ወሰዷቸው። መናገሻ ውስጥ በአፄ በካፋ ጽራግ ማሰሬነት ማዕረግ የተሾሙትንና ቤተመንግሥት ተቀማጭ የሆኑትን ንጉሥ አንጋሹ መነኩሴ ማሞ፣ ቡራኬ ሰጪው
ቄስ እልፍዮስ፣ የመናገሻ ግንብ አጋፋሪዎች አቡሊዲስ፣ ገላውዲዎስ፣ አደሩና ሌሎችም ባሉበት ምንትዋብ ዙፋን ላይ ስትቀመጥ ኢያሱ እግሯ ሥር ተቀመጠ። ኢያሱ ነገሩ እምብዛም ባይገባውም አባቱ እንደሞቱና ሊነግሥ መሆኑ ስለተነገረው የንግሥናው ደስታ ሳይሆን
የአባቱ ሞት ሐዘን ፊቱ ላይ ይታያል።
የንግሥ ሥርዐቱን ለመጀመር በጅሮንድ አብርሃም ዘውዱን ለጽራግ ማሰሬ ማሞ አቀረቡ። ጽራግ ማሰሬ ማሞም ዘውዱን አፄ በካፋ ዙፋን ላይ አስቀመጡ። ንጉሥ ሲነግሥ የሚጸለየውን ጸሎት ጸለዩ።ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከብሉያትና ከሐዲስ ኪዳንም የተመረጡ ምንባቦችን አነበቡ። አቡነ ዘበሰማያትም ደገሙ። ኢያሱን ወደ እሳቸው አምጥተው
እጃቸውን አናቱ ላይ አስቀምጠው በአንብሮተ እድ ባረኩት፣ ጸለዩለት፡-
“አቤቱ ፍርድህን ለንጉሡ ስጠው
እውነትኸንም ለንጉሡ ልጅ
ሕዝብኸን በእውነት ይፈርድላቸው ዘንድ
ድኾችኸንም በፍትሕ ይገዛ ዘንድ
አድባር አውጋሩ የሕዝብኸን ሰላም ይቀበሉ።
ከዚያም መከሩት፣
ኰንን በጽድቅ ነዳያነ ሕዝበከ
ወአድኅኖሙ ለደቂቀ ምስኪናኒከ
ወአሕስሮ ለዕቡይ
ተስፋም ሰጡት፡-
በዘመኑ እውነት ይሠርጻል
ከባሕር እስከ ባሕርም ይገዛል
ከወንዞችም እስከ ዓለም ጥጋጥግ
ኢትዮጵያ ይገዙለታል
ጠላቶቹ ግን አፈር ይበላሉ።”
ከዚህና ከበርካታ ሌሎች ጸሎቶች በኋላ፣ በዕንቁ ያጌጠውን የአባቱን
ዘውድ ራሱ ላይ ደፉለት፣ በአባቱ ዙፋንም ላይ አስቀመጡት። ከዚያም የጫነው ዘውድ ለጌጥ የተሠራ ሳይሆን የሕዝቡን ችግርና መከራ የሚሸከምላቸው መሆኑን የሚዘክር፣ ንጉሣቸውና አገልጋያቸው መሆኑን
የሚያሳስብ እንደሆነ ተናግረው መረቁት፡ አስመረቁት፡-
“ሺሕ ዓመት ንገሥ
ወንድ ልጅ ለፈረስ፣ ሴት ልጅ ለበርኖስ አድርስ።”
አሉት፤ በዚያው የተሰበሰው ሕዝብም ይህንን ሦስት ጊዜ መላልሰው በአንድ ድምጽ አስተጋቡ።
“ዳዊት ቤት ቀርነ መድኃኒት የሆነ ንጉሥ ስላነሳልን እግዚአብሔር
ይመስገን፤” አሉ፣ ጽራግ ማሰሬ ማሞ።
ኢያሱ ዳግማዊ ኢያሱ ንጉሠ ነገሥት ተብሎ ነገሠ።
ጽራግ ማሰሬ ማሞ ዙፋኑ ስር ተንበርክከው ሰገዱለት። በዓሉ ላይ ተገኝቶ የነበረው ሁሉ ተነስቶ ለሰባት ዓመቱ ልጅ ለኢያሱ ሰገደ።
በተራው ንጉሥ ባራኪው እልፍዮስ ወደ ኢያሱ ተጠግተው የብዙ
ታላላቅ ነገሥታት ነብያትና ታላላቅ ነገስታት በረከት እንዲያድርበት መረቁት።
“የቅዱስ ዳዊት በረከት ይደርብህ። የጠቢቡ ሰለሞን ፍትሕና ጥበብ አይለይህ። የኢዮሲያስ፣ የሕዝቅያስና የቆስጠንጢኖስ በረከት ይደርብህ”እያሉ ባረኩት። በመጨረሻም ለኢያሱ ዳግመኛ ሰግደው ወደነበሩበት ተመለሱ። ዘውዱ ለትንሹ ኢያሱ ከባድ በመሆኑ ጽራግ ማሰሬ ማሞ
ከራሱ ላይ አንስተውለት በክብር ጠረጴዛው ላይ አኖሩት::
ምንትዋብ ከተቀመጠችበት ተነስታ እጆቿን ዘርግታ፣ “እኔን
ታናሺቱን ለዝኸ ክብር ላበቃኝ እዝጊሃር ምስጋና ይግባው። ፈጣሪዬ ሆይ ለኔ ለባርያህ በንጉሡ በአባቱ በአጤ በካፋ ዙፋን ላይ መቀመጥ ዘር
ስለሰጠኸኝ ክብር ምስጋና ይግባህ” ብላ ምስጋና አቀረበች። በኋላም ኢያሱን ላነገሠው ለጽራግ ማሰሬ ማሞ፣ ለአንጋሽ እንደሚደረገው አስር ሰቅለ ወርቅ እንዲሰጥ ትዕዛዝ አስተላለፈች።
ትውፊቱን ጥሳ፣ የልጇ ንግሥ ላይ ባሏን ያነገሡት አቡነ ክርስቶዶሌ
ተገኝተው ዘውድ እንዲጭኑለት እንኳን ሳታደርግ፣ መፈጸም ያለባቸውን ዋና ዋና ጉዳዮች ብቻ ፈጽማ የኢያሱ የንግሥ ሥርዐት በምሥጢር ያለአንዳች ኮሽታ ተጠናቀቀ።
ወዲያው ባሻ ኤልያስን አስጠርታ፣ ሲነጋ የንጉሠ ነገሥቱ ሕልፈትና
የኢያሱ መንገሥ እንዲታወጅና ለንጉሥ ቀብር የሚደረገውን ሥርዐት ሁሉ እንዲያደርግ አዘዘችው። እጅ ነስቶ ሄደ።
ጠዋት ላይ፣ በታዘዙት መሠረት እነባሻ ኤልያስ ድብ አንበሳ ይዘው
ወደ ጃን ተከል ወረዱ። ሊጋባው፣ ከአዛዡ በተቀበለው ትዕዛዝ መሠረት ነጋሪት እየጎሰመ፣ “አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ! የሞትንም እኛ፣ ያለንም እኛ ንጉሥ በካፋ ዐርፈዋል። ልጃቸው ኢያሱ ነግሠዋል፣ የሰማ ላልሰማ
ያሰማ። ጠላቶቻችን ይፈሩ፤ ወዳጆቻችን ትፍሥሕት ያድርጉ፣ ባለህበት እርጋ፤ ነጋዴም ነግድ፤ ገበሬም እረስ!” እያለ አዋጅ ነገረ።
ጐንደሬዎች ግልብጥ ብለው ወጡ። “ይበጅ! ይበጅ! ያድርግ!”
አሉ። በኢያሱ መንገሥ ተደሰቱ፤ እምብዛም ባይወዷቸውም ለበካፋም አለቀሱ።
👍13
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
... አየ ወለቴ ጠጋ ብየ ባጥናናሁሽ፡፡ እኔ አልረሳሁሽም። የሩቅ ቅርብ ሁኜ ስላንቺ አስባለሁ። ምንግዝየም ኸልቤ አትጠፊም አለ።..
ከለቅሶው በኋላ፣ ሕዝቡ ወደ መኻል ግንብ ለስንብት ሲሄድ አብሮ ሄደ። በግርግሩ መሃል ከነአብርሃ ጋር በመጠፋፋቱ፣ ከተሰናዳው የእዝን ግብር ከሕዝቡ ጋር መካፈል ሆዱ እንቢ ብሎት፣ በሰዎች ተከልሎ ምንትዋብና ኢያሱን እጅ ነስቶ አልፎ ወርቄ ቤት ሄዶ ውጭ ተቀምጦ ጠበቃቸው።
እነወርቄ እንደተመለሱ፣ አብርሃ ለብቻው ከተፍ አለ። “የት ኸዳችሁ
ነው የተጠፋፋን? ወዲህ ብል ወዲያ ብል አጣኋችሁ” አላቸው።
ሁሉም የነበሩበትን ቦታ ከተነጋገሩ በኋላ፣ ውስጥ ገብተው ወርቄ
ምሳ አቀረበች። በልተው ሲጨርሱ፣ ጠላ እየተጎነጩ ስለ ቀኑ ውሎ ማውጋት ጀመሩ።
“መቼም ሰዉ ሁሉ ሚያወራው ስለ እቴጌ ጥንካሬ ነው” አለ፣
አብርሃ። “ቀብሩን ሆነ የቅጥር ልቅሶውን እንዴት አርገው እንዳዘጋጁት ይገርማል ። ባላባቱ፣ ካህናቱና ሊቃውንቱ፣ “በርግጥም በካፋ አልሞቱም ሲሉ ነበር አሉ” አላቸው።
ጥላዬ ዝም አለ። ምንትዋብ በልጅነቷ ባሏን በማጣቷ ጉዳቷ
ተሰምቶታል። አጠገቧ ሆኖ ሊያጽናናት ባይችልም፣ ደብረ ወርቅ መመለስ ከብዶታል። በሩቅም ቢሆን ሐዘኗን መካፈል መርጧል።ምንም ቢሆን ወለቴ እኮ አብሮ አደጌ ናት። ኑሯችን እየቅል ቢሆንም በዕዘኗ ሆነ በደስታዋ የሩቅ ቅርብ ሁኜ መካፈል አለብኝ አለ፣ ለራሱ።
በሌላ በኩል አለቃ ሔኖክን ደግሞ ሳያያቸው ማረፋቸው አሳዘነው።
ደብረ ወርቅ በነበረበት ወቅት ስለእሳቸው ሲያስብ፣ የተማረውን ሁሉ ሊያወራቸው ሲመኝ ቆይቶ፣ እንደ አባት የሚያያቸውን መምህሩን ሞት ስለነጠቀው ከፋው። በሌላ በኩል ወርቄ ወላጆቿ መጥተውላት አጠገቧ
በመሆናቸው ደስ አለው። አርባቸውን ሳላወጣ አልኸድም አለ፣ ለራሱ።
ወርቄ፣ ሐሳብ ውስጥ እንደገባ አስተዋለች። ደብረ ወርቅ እስኪመለስ ድረስ የቀድሞ ቤቱ መክረም እንደሚችል ነገረችው።
አብርሃ፣ ጥላዬን ከስድስት ዓመት በኋላ፣ በማግኘቱ ደስታው መጠን
አጥቶ ነበርና፣ “ኸኔ ዘንድ ይቆያል” አላት።
እኔማ ያው ቤቱ አለ ብየ እንጂ” አለች ወርቄ፣ ጥላዬን እያየች።
“ኸብረሃም ዘንድ እየተጫወትን እንከርማለን። ኸናንተም አልለይም።አልሰማሁ ሁኘ አለቃን ሳልቀብራቸው ቀርቸ እኼው ዛሬ እንጉሥ ለቅሶ ለመድረስ በቃሁ። እንዳው አለቃን ከዛሬ ነገ አያቸዋለሁ ስል አመለጡኝ” አላት።
ወርቄ በዐይኗ ውሃ ሞላ።
“ተይ ልዤ ጠሐይ ላይ ውለሽ መጥተሽ። መቀበል ነው እንጂ ሌላ ምን ማረግ ይቻላል?” አሏት እናቷ።
አብርሃ፣ ትኩር ብሎ አያትና፣ “የአለቃ ሞት ሁላችንንም ነው የጎዳ።መጥናናት ነው እንጂ ሌላ ምን እናረጋለን። ሞት እንደሁ ያለ ነው” አላት።
“የአለቃን ነፍስ በገነት ያኑርልን። የጃንሆይንም ነፍስ እዝጊሃር
ይማር” አሉ፣ የወርቄ አባት።
“አሜን” አሉ፣ ሁለም።
“እቴጌም ቢሆኑ አሳዘኑኝ በልዥነታቸው ባላቸውን አጥተው። ዕጣ ፈንታቸው እንደኔ የሙት ሚስት መሆኑ ያሳዝናል” አለች ወርቄ ለምንትዋብም ለራሷም በማዘን።
ሁሉም አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሉ።
አብርሃ፣ እኔማ ትምርቱስ እንዴት ሁኖለት ይሆን እያልሁ ሳስብ”
አለው ጥላዬን፣ ቤቱን የከበበውን የትካዜ ድባብ ለመቀየር።
“ትምርቱማ... ያው ኸዝኽ አንድ ዓመት አርጌ ማልነበር ወደ ደብረ
ወርቅ ማርያም የኸድሁት? ኸዛ ያገኘዃቸው መምህር... ሊቀጠበብት አዳሙ እንዴት ያሉ ሰው መሰሉህ። አለቃ ሔኖክ እሳቸው ዘንድ ስለላኩኝ እንዳመሰገንዃቸው አለሁ። ያው... ኸዝኸ እንደኸድሁ ሥጋ
ለባሾችን ሠራሁ።”
“ሰዎችን ማለቱ ነው” ሲል አብራራ አብርሃ፣ የወርቄ ወላጆች ግር
ሲላቸው አይቶ።
“ቤተስኪያን አካባቢ ያሉ ቀሳውስት፣ መነኮሳት... መምህር
የመሳሰሉትን ማለቴ ነው” አለ፣ ጥላዬ። “ታስታውሳለህ አለቃ ሔኖክ...ነፍሳቸውን ይማርና... ስዠምር ጥቁር ቀለም ብቻ ነው ምትጠቀመው ሲለኝ? ኋላ ሌሎች ዓይነት ቀለሞችም ተጠቅሜያለሁ።”
“ራስህ እያዘጋጀህ?"
ኋላ! ራስህ ነህ እንጂ ሌላ ማን ያዘጋጅልሀል? እና ... የቤተክህነት
ሰዎችን ስትሥል፣ የልብሳቸውን ሆነ የካባቸውን ቀለም አሳምረህ
ትሠራለህ። ጥምጥማቸውንም እንዲሁ ትክክል አርገህ ትሥላለህ። ንድፉ እንዳይንጋደድብህም ትጠነቃቃለህ። የልብሳቸውንና የካባቸውንም ዕጥፋት ሳይቀር ነው በጥንቃቄ ምትሠራው።”
“ስንታቸውን ሣልህ በል?”
“ምን አለፋህ ብዙዎቹን ሥያለሁ። የዠመርሁት በአንድ መነኩሴ
ነበር። መነኩሴው ሲያዩት ደስ አላቸው። ማስታወሻ ብየ ሰጠኋቸው።ሁለተኛ ሊቀጠበብት አዳሙን ነበር የሣልሁት። እሳቸውም እንደዝሁ ደስ አላቸው። እንዲህ እያልሁ ወደሚቀጥለው ተሻገርሁ።”
“ምን ሠራህ?”
“ጻድቃንን ሣልሁ። አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ቅዱስ ያሬድን፣ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን፣ አቡነ ኪሮስን፣ እናታችንን ክርስቶስ ሣምራን የመሰሉትን ሣልሁ።”
“የሁሉን መልክ አውቃችሁ ነው ምትሥሉ?” ሲሉ ጣልቃ ገቡ፣
የወርቄ አባት።
“የለ... የለ... እነሱን ስንሥል መልካቸውን ስለማናውቅ... የተሰወሩ ስላለባቸውም ... ታሪካቸውን፣ ታምራቸውንና ገድላቸውን ጠንቅቀን
አውቀን ነው ምንሥል። እነሱን ለመሣል ኸመነሣታችን በፊት
ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለማወቅ ንባብ አድርገን ነው ምንሥላቸው።
ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ስንሠራ ደሞ ትክክለኛ መልካቸው
ይገለጥልናል” አላቸው፣ ጥላዬ።
“እህ” አሉ የወርቄ አባት፣ እንደገባቸው ለማሳወቅ ራሳቸውን
እየነቀነቁ።
“እንደ ቅኔ ነው በለኛ! እኛም እኮ ክብረ ነገሥት፣ ገድላት፣ ድርሳናት
ወንጌል... መጽሐፍ ቅዱስ... ኻላወቅን ቅኔ አንቆጥርም” አለው
አብርሃ።
“አውቀው የለ። ደሞ ሰማዕታትን ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እንደ መርቆርዮርስና ገላውዲዮስ የመሳሰሉትን ሣልሁ። ሰማዕታት ቤተክሲያን ውስጥ ሲሣሉ በግራ በኩል ነው ሚሣሉ። ሁሉም ሚሣሉበት ቦታ ቦታ አላቸው። ሚሣሉበት ቀለምም እንደዝሁ ይለያያል። ሰማዕታት ለጌታችን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለአዳኝነቱ ሲመሰክሩ አንገታቸው
በሠይፍ ተቀልቶ፣ ወይ ከእሳት እቶን ተጥለው ማዶል የሞቱት? እናም ያነን ያፈሰሱትን ደም ለመዘከር በቀይ ቀለም ይሣላሉ። መላዕክት የመንፈስ ቅዱስ ሕይወት በነሱ ላይ ስላደረ... ብርሃንና ተስፋ ሰጪዐስለሆኑ፣ እነሱን ለመሣል ምትጠቀመው ቀለም ደማቅ መሆን አለበት።
ደማቅ ቀለም የተስፋ ምልክት ነው። ጻድቃን.. ይኸን ዓለም ንቀው በጽድቅ ኖረው ያለፉ አባቶቻችን ደሞ ፈዘዝ ባለ ቀለም ይሣላሉ።ድንግል ማርያም ደሞ ልብሷ ከላይ በሰማያዊ፣ ከውስጥ በቀይና ምትከናነበው ደሞ በአረንጓዴ ቀለሞች ይሣላል። ምትሥለው ሥዕል
እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል። ሰማያዊ መንፈሳዊ ንፅህናን ያሳያል፤ ነጭ እንደምታውቀው ብርሃን ነው፤ ብጫ
ደሞ የዠግንነት ምልክት ነው።”
“ዘይገርም!” አለ፣ አብርሃ።
“ምን አለፋህ መላዕክትን... ሰባቱን ሊቃነ መላዕክት... እነቅዱስ ገብርኤልንም ሣልሁ” ሲል ቀጠለ ጥላዬ። “መላዕክት እንደምታውቀው መከሠቻ አላቸው። ሚከሠቱበት መንገድም ይለያያል...”
“መከሠቻ?” አሉ፣ ሁሉን በጥሞና ሲያዳምጡ የቆዩት የወርቄ እናት።
“ኣዎ መገለጫ ማለቴ ነው።”
“እንዴት እንዴት ሁነው ነው ሚገለጡ?”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
... አየ ወለቴ ጠጋ ብየ ባጥናናሁሽ፡፡ እኔ አልረሳሁሽም። የሩቅ ቅርብ ሁኜ ስላንቺ አስባለሁ። ምንግዝየም ኸልቤ አትጠፊም አለ።..
ከለቅሶው በኋላ፣ ሕዝቡ ወደ መኻል ግንብ ለስንብት ሲሄድ አብሮ ሄደ። በግርግሩ መሃል ከነአብርሃ ጋር በመጠፋፋቱ፣ ከተሰናዳው የእዝን ግብር ከሕዝቡ ጋር መካፈል ሆዱ እንቢ ብሎት፣ በሰዎች ተከልሎ ምንትዋብና ኢያሱን እጅ ነስቶ አልፎ ወርቄ ቤት ሄዶ ውጭ ተቀምጦ ጠበቃቸው።
እነወርቄ እንደተመለሱ፣ አብርሃ ለብቻው ከተፍ አለ። “የት ኸዳችሁ
ነው የተጠፋፋን? ወዲህ ብል ወዲያ ብል አጣኋችሁ” አላቸው።
ሁሉም የነበሩበትን ቦታ ከተነጋገሩ በኋላ፣ ውስጥ ገብተው ወርቄ
ምሳ አቀረበች። በልተው ሲጨርሱ፣ ጠላ እየተጎነጩ ስለ ቀኑ ውሎ ማውጋት ጀመሩ።
“መቼም ሰዉ ሁሉ ሚያወራው ስለ እቴጌ ጥንካሬ ነው” አለ፣
አብርሃ። “ቀብሩን ሆነ የቅጥር ልቅሶውን እንዴት አርገው እንዳዘጋጁት ይገርማል ። ባላባቱ፣ ካህናቱና ሊቃውንቱ፣ “በርግጥም በካፋ አልሞቱም ሲሉ ነበር አሉ” አላቸው።
ጥላዬ ዝም አለ። ምንትዋብ በልጅነቷ ባሏን በማጣቷ ጉዳቷ
ተሰምቶታል። አጠገቧ ሆኖ ሊያጽናናት ባይችልም፣ ደብረ ወርቅ መመለስ ከብዶታል። በሩቅም ቢሆን ሐዘኗን መካፈል መርጧል።ምንም ቢሆን ወለቴ እኮ አብሮ አደጌ ናት። ኑሯችን እየቅል ቢሆንም በዕዘኗ ሆነ በደስታዋ የሩቅ ቅርብ ሁኜ መካፈል አለብኝ አለ፣ ለራሱ።
በሌላ በኩል አለቃ ሔኖክን ደግሞ ሳያያቸው ማረፋቸው አሳዘነው።
ደብረ ወርቅ በነበረበት ወቅት ስለእሳቸው ሲያስብ፣ የተማረውን ሁሉ ሊያወራቸው ሲመኝ ቆይቶ፣ እንደ አባት የሚያያቸውን መምህሩን ሞት ስለነጠቀው ከፋው። በሌላ በኩል ወርቄ ወላጆቿ መጥተውላት አጠገቧ
በመሆናቸው ደስ አለው። አርባቸውን ሳላወጣ አልኸድም አለ፣ ለራሱ።
ወርቄ፣ ሐሳብ ውስጥ እንደገባ አስተዋለች። ደብረ ወርቅ እስኪመለስ ድረስ የቀድሞ ቤቱ መክረም እንደሚችል ነገረችው።
አብርሃ፣ ጥላዬን ከስድስት ዓመት በኋላ፣ በማግኘቱ ደስታው መጠን
አጥቶ ነበርና፣ “ኸኔ ዘንድ ይቆያል” አላት።
እኔማ ያው ቤቱ አለ ብየ እንጂ” አለች ወርቄ፣ ጥላዬን እያየች።
“ኸብረሃም ዘንድ እየተጫወትን እንከርማለን። ኸናንተም አልለይም።አልሰማሁ ሁኘ አለቃን ሳልቀብራቸው ቀርቸ እኼው ዛሬ እንጉሥ ለቅሶ ለመድረስ በቃሁ። እንዳው አለቃን ከዛሬ ነገ አያቸዋለሁ ስል አመለጡኝ” አላት።
ወርቄ በዐይኗ ውሃ ሞላ።
“ተይ ልዤ ጠሐይ ላይ ውለሽ መጥተሽ። መቀበል ነው እንጂ ሌላ ምን ማረግ ይቻላል?” አሏት እናቷ።
አብርሃ፣ ትኩር ብሎ አያትና፣ “የአለቃ ሞት ሁላችንንም ነው የጎዳ።መጥናናት ነው እንጂ ሌላ ምን እናረጋለን። ሞት እንደሁ ያለ ነው” አላት።
“የአለቃን ነፍስ በገነት ያኑርልን። የጃንሆይንም ነፍስ እዝጊሃር
ይማር” አሉ፣ የወርቄ አባት።
“አሜን” አሉ፣ ሁለም።
“እቴጌም ቢሆኑ አሳዘኑኝ በልዥነታቸው ባላቸውን አጥተው። ዕጣ ፈንታቸው እንደኔ የሙት ሚስት መሆኑ ያሳዝናል” አለች ወርቄ ለምንትዋብም ለራሷም በማዘን።
ሁሉም አንገታቸውን ደፍተው ዝም አሉ።
አብርሃ፣ እኔማ ትምርቱስ እንዴት ሁኖለት ይሆን እያልሁ ሳስብ”
አለው ጥላዬን፣ ቤቱን የከበበውን የትካዜ ድባብ ለመቀየር።
“ትምርቱማ... ያው ኸዝኽ አንድ ዓመት አርጌ ማልነበር ወደ ደብረ
ወርቅ ማርያም የኸድሁት? ኸዛ ያገኘዃቸው መምህር... ሊቀጠበብት አዳሙ እንዴት ያሉ ሰው መሰሉህ። አለቃ ሔኖክ እሳቸው ዘንድ ስለላኩኝ እንዳመሰገንዃቸው አለሁ። ያው... ኸዝኸ እንደኸድሁ ሥጋ
ለባሾችን ሠራሁ።”
“ሰዎችን ማለቱ ነው” ሲል አብራራ አብርሃ፣ የወርቄ ወላጆች ግር
ሲላቸው አይቶ።
“ቤተስኪያን አካባቢ ያሉ ቀሳውስት፣ መነኮሳት... መምህር
የመሳሰሉትን ማለቴ ነው” አለ፣ ጥላዬ። “ታስታውሳለህ አለቃ ሔኖክ...ነፍሳቸውን ይማርና... ስዠምር ጥቁር ቀለም ብቻ ነው ምትጠቀመው ሲለኝ? ኋላ ሌሎች ዓይነት ቀለሞችም ተጠቅሜያለሁ።”
“ራስህ እያዘጋጀህ?"
ኋላ! ራስህ ነህ እንጂ ሌላ ማን ያዘጋጅልሀል? እና ... የቤተክህነት
ሰዎችን ስትሥል፣ የልብሳቸውን ሆነ የካባቸውን ቀለም አሳምረህ
ትሠራለህ። ጥምጥማቸውንም እንዲሁ ትክክል አርገህ ትሥላለህ። ንድፉ እንዳይንጋደድብህም ትጠነቃቃለህ። የልብሳቸውንና የካባቸውንም ዕጥፋት ሳይቀር ነው በጥንቃቄ ምትሠራው።”
“ስንታቸውን ሣልህ በል?”
“ምን አለፋህ ብዙዎቹን ሥያለሁ። የዠመርሁት በአንድ መነኩሴ
ነበር። መነኩሴው ሲያዩት ደስ አላቸው። ማስታወሻ ብየ ሰጠኋቸው።ሁለተኛ ሊቀጠበብት አዳሙን ነበር የሣልሁት። እሳቸውም እንደዝሁ ደስ አላቸው። እንዲህ እያልሁ ወደሚቀጥለው ተሻገርሁ።”
“ምን ሠራህ?”
“ጻድቃንን ሣልሁ። አቡነ ተክለሃይማኖትን፣ ቅዱስ ያሬድን፣ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን፣ አቡነ ኪሮስን፣ እናታችንን ክርስቶስ ሣምራን የመሰሉትን ሣልሁ።”
“የሁሉን መልክ አውቃችሁ ነው ምትሥሉ?” ሲሉ ጣልቃ ገቡ፣
የወርቄ አባት።
“የለ... የለ... እነሱን ስንሥል መልካቸውን ስለማናውቅ... የተሰወሩ ስላለባቸውም ... ታሪካቸውን፣ ታምራቸውንና ገድላቸውን ጠንቅቀን
አውቀን ነው ምንሥል። እነሱን ለመሣል ኸመነሣታችን በፊት
ታሪካቸውንና ገድላቸውን ለማወቅ ንባብ አድርገን ነው ምንሥላቸው።
ሥጋ ወደሙን ተቀብለን ስንሠራ ደሞ ትክክለኛ መልካቸው
ይገለጥልናል” አላቸው፣ ጥላዬ።
“እህ” አሉ የወርቄ አባት፣ እንደገባቸው ለማሳወቅ ራሳቸውን
እየነቀነቁ።
“እንደ ቅኔ ነው በለኛ! እኛም እኮ ክብረ ነገሥት፣ ገድላት፣ ድርሳናት
ወንጌል... መጽሐፍ ቅዱስ... ኻላወቅን ቅኔ አንቆጥርም” አለው
አብርሃ።
“አውቀው የለ። ደሞ ሰማዕታትን ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ እንደ መርቆርዮርስና ገላውዲዮስ የመሳሰሉትን ሣልሁ። ሰማዕታት ቤተክሲያን ውስጥ ሲሣሉ በግራ በኩል ነው ሚሣሉ። ሁሉም ሚሣሉበት ቦታ ቦታ አላቸው። ሚሣሉበት ቀለምም እንደዝሁ ይለያያል። ሰማዕታት ለጌታችን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ፣ ስለአዳኝነቱ ሲመሰክሩ አንገታቸው
በሠይፍ ተቀልቶ፣ ወይ ከእሳት እቶን ተጥለው ማዶል የሞቱት? እናም ያነን ያፈሰሱትን ደም ለመዘከር በቀይ ቀለም ይሣላሉ። መላዕክት የመንፈስ ቅዱስ ሕይወት በነሱ ላይ ስላደረ... ብርሃንና ተስፋ ሰጪዐስለሆኑ፣ እነሱን ለመሣል ምትጠቀመው ቀለም ደማቅ መሆን አለበት።
ደማቅ ቀለም የተስፋ ምልክት ነው። ጻድቃን.. ይኸን ዓለም ንቀው በጽድቅ ኖረው ያለፉ አባቶቻችን ደሞ ፈዘዝ ባለ ቀለም ይሣላሉ።ድንግል ማርያም ደሞ ልብሷ ከላይ በሰማያዊ፣ ከውስጥ በቀይና ምትከናነበው ደሞ በአረንጓዴ ቀለሞች ይሣላል። ምትሥለው ሥዕል
እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል። ሰማያዊ መንፈሳዊ ንፅህናን ያሳያል፤ ነጭ እንደምታውቀው ብርሃን ነው፤ ብጫ
ደሞ የዠግንነት ምልክት ነው።”
“ዘይገርም!” አለ፣ አብርሃ።
“ምን አለፋህ መላዕክትን... ሰባቱን ሊቃነ መላዕክት... እነቅዱስ ገብርኤልንም ሣልሁ” ሲል ቀጠለ ጥላዬ። “መላዕክት እንደምታውቀው መከሠቻ አላቸው። ሚከሠቱበት መንገድም ይለያያል...”
“መከሠቻ?” አሉ፣ ሁሉን በጥሞና ሲያዳምጡ የቆዩት የወርቄ እናት።
“ኣዎ መገለጫ ማለቴ ነው።”
“እንዴት እንዴት ሁነው ነው ሚገለጡ?”
👍11
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ይደልዎ ይደልዎ”
ምንትዋብ፣ ኢያሱ በነገሠ በሁለተኛው ወር ረጅም ነጭ ሐር ቀሚስ ለብሳ፣ በወርቅና በዕንቁ የተንቆጠቆጠ ካባ በላዩ ላይ ደርባ፣ በወርቅ አጊጣ፣ ፊቷን በነጭ ዐይነ ርግብ ከልላ፣ የወርቅ በትረ መንግሥት ጨብጣና ከወርቅ የተሠራ ነጠላ ጫማ ተጫምታ ተሸልማ በወጣችው
በቅሎዋ ላይ ተሰይማ፣ የንግሥ ሥርዐት ወደሚፈጸምበት ወደ መናገሻ ግንብ አመራች።
መናገሻ ግንብ ውስጥ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ አዛዦች፣ ካህናት፣ ሊቃውንትና ወይዛዝርት
እንደየማዕረጋቸው ቦታቸውን ይዘው የንጉሥ መሞት የሚያመጣውን ቀውስ ጠንቅቃ
የምታውቀው ምንትዋብ፣ አክሱም ጽዮን የሚደረገውን ሁለተኛውን
የኢያሱን የንግሥ ሥርዐት አስቀርታ በነገሠ በወሩ ብርሃን ሰገድ የሚል ስመ መንግሥት ከተሰጠው ከዳግማዊ ኢያሱና ከቤተሰቦቿ ጋር ስትገባ ሁሉ ተነሥቶ እጅ ነሳ።
በወርቅ ያጌጠውን የአባቱን ዘውድ የጫነውና የእሳቸውን የወርቅ
በትረ መንግሥት የጨበጠው ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “እናቴን አንግሡልኝ፣ መንግሥቴ ያለሷ አይጠናም” ሲል ተሰብሳቢዎቹ፣ “ይደልዎ ይደልዎ! ይገባታል! ይገባታል! ጎበዝ ክርስቲያን፣ አዋቂ ናት። ሽህ ዓመት ንገሥ። የቆስጦንጢኖስን ምሽት
እሌኒን ትመስላታለች” አሉ።
አንጋሹ ጽራግ ማሰሬ ማሞ ከዕንቁ፣ ከወርቅና ከብር የተሠራውንና በሻሽ ተሸፍኖ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠውን የአፄ ሚናስ የነበረውን ዘውድ አንስተው ምንትዋብ ራስ ላይ ጭነውላት ሲያበቁ ዝቅ ብለው ሰገዱላት፣ ከኢያሱ ቀኝም አስቀመጧት።
ባራኪው እልፍዮስ፣ “እዝጊሃር ክፉዎችን እንዲያሸንፉ ኃይል ይስጥዎ። ክብርዎን ያብዛልዎ። ፈሪሐ እዝጊሃርን በልብዎ ያሳድርልዎ። አቤቱ አምላካችን ሆይ! በአገልጋይህ በእቴጌ ምንትዋብ ላይ እኼን የደስታና
የክብር ዘውድ አኑር፤ እኼውም የቸርነት፣ የርህራሄ፣ የዕውቀትና የጥበብ ዘውድ ይሁንላቸው” ብሎ ሲባርካት፣ ከኋላዋ ቆመው የነበሩት ሴት የመሣፍንት ዘሮችና ወይዛዝርት ዕልልታውን አቀለጡት።
ምንትዋብ ለአምላኳ በልቧ ምስጋና አቀረበች።
ካህናት ዘመሩ፣ ወረቡ፣ ሊቃውንቱ ቅኔ አወረዱ። እንደ ንግሥተ
ሳባ፣ እቴጌ እሌኒ፣ እቴጌ ሰብለወንጌልና እቴጌ መስቀል ክብራን የመሳሰሉ የታላላቅ ሴቶች ስም እየጠቀሱ አሞካሿት። “አንቺ እሌኒ ማለት ነሽ። ልዥሸን ብርሃን ሰገድ ኢያሱን ኸጎኑ ሁነሽ እንደምትረጂው አንጠራጠርም” ሲሉ እሷ ላይ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገለፁላት።
ምንትዋብ፣ አባቷ ዕጣ ፈንታ፣ እናቷ ዕድል አያቷ ግን የተገባት ያሉትን ስትጎናፀፍ ተስተዋለ።
ሕይወት ሲሻት ለጋሥ መሆኗን አስመሰከረች።
ባለ ክራሩና ባለ መሰንቆው የውዳሴና የሙገሳ ግጥም ሲያንቆረቁር፣ፎካሪው በቀረርቶ፣ ሽላዩ በሽለላ የበኩሉን ምስጋና አበረከተ። አንዱ ሀሚና ተነሰቶ በመሰንቆ፣
በወለተጴጥሮስ ተወልዳ በንግርት፣
በእዝጊሄር ፈቃድ በነብያት ትንቢት፤
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ያገራችን ውበት፤
የምታስተባብር ጥድቅ ተሃይማኖት፣
ዳር ድንበር ጠባቂ ያባቶቿን ርስት፣
ኸዝኸ በላይ ጠጋ ኻአምላክ መሰጠት፣
ምንድን ሊሰጧት ነው ምንትዋብ ሚሏት?
እያለ ሲያሞግሳት፣ የተሰበሰበው ሰው ደግሞ እሱን አመሰገነው።
ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መለከት እየተነፋ ከመናገሻ ግንብ በደጅ
አጋፋሪው አቀናባሪነት የፊቱን ወጀብ ሰንደቅ የያዙ፣ የእልፍኝ አሽከሮች፣ባለሟሎችና ሠይፈ ጃግሬዎች ፈንጠር ብለው እየመሩ፣ የመሃል ዐጀቡ
በእልፍኝ አስከልካዩ እየተጠበቀ፣ ኢያሱና ምንትዋብ ጎን ለጎን ሆነው
ድባብ ተይዞላቸው፣ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ ሊቃውንት፣ ወይዛዝርት፣ግራዝማቾች፣ ቀኛዝማቾችና የጦር አበጋዞች እንደየደረጃቸው ከኋላ
እያጀቧቸው፣ ሰልፍ አስከባሪዎቹና የንጉሠ ነገሥቱ ጠባቂ የሆኑት ጋሻዐጃግሬዎቹ ተከትለው የሰልፉን ግራና ቀኝ አንጋቾች እየጠበቁ ራስ ቢትወደዱ በመጨረሻ ተሰልፈው ነገሥታቱ በዘፈንና በጭፈራ ከግቢ
ሲወጡ ካህናት፣
መንክር ግርማ መንክር ግርማ
ወልደልዑል ጸለላ መንክር ግርማ
የምትደንቅ ግርማ ሞገስን
የምትደንቅ ግርማ ሞገስ
የወልደልዑል ልጅ፣ እጅግ የላቀው አባት ልጅ፤
እያሉ፣ ምንትዋብ በወንድሟ በወልደልዑል መከታነት መንገሧን
በቅኔ ጠቅ እያደረጉ በፀናፅልና በከበሮ ዐጀቧት።
ዘውዷን እንደጫነች በቅሎዋ ላይ ተሰይማና ታጅባ፣ ወደ ሕዝቡ
አመራች። ከጐንደርና ከአካባቢዋ የመጣው ነፍጠኛ፣ ገበሬ፣ እረኛ፣
ነጋዴ፣ ወታደር፣ አንጥረኛ፣ ሸማኔ፣ ቆዳ አልፊ፣ ጥልፍ ጠላፊ፣ ሹሩባ ሠሪ መድኃኒት አዋቂ፣ ወጌሻ፣ የቤት እመቤት፣ አረቄና ጠላ ሻጭ፣ ዲያቆን ተማሪ ፣ የቁም ጸሐፊ፣ ሠዓሊ፣ ብራና ሠሪ፣ ባለክራሩና ባለመሰንቆው
ሴቱ ሹሩባውን አንዠርጎ፣ ነጠላውን አጣፍቶ፣ ወገቡን በድግ ደግፎ ማተቡ ላይ የእንጨት መስቀሉን፣ ድሪውን፣ ጨሌውን፣ ዶቃውን ቁርጭምጭሚቱ ዙርያ አልቦውን፣ የእጁ አንጓ ላይ አንባሩን ደርድሮ ገሚሱ የቀርከሀ ጃንጥላውን አጥልቶ፣ ወንዱ ፀጉሩን አጎፍሮ፣ ለምዱን ደርቦ፣ ዱላውን ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ፣ ልጆች ጥብቋቸውን
አጥልቀው፣ ክታባቸውን አንጠልጥለው ምንትዋብ ከኢያሱ ጋር ጃን ተከል ብቅ ስትል አካባቢው ድብልቅልቁ ወጣ።
ሴቶች በዕልልታና በእስክስታ፣ ወንዶች በሆታና በጭፈራ አካባቢውን አናጉት፤ ካህናት በሽብሸባ አደመቁት። እነምንትዋብ ካለፉ በኋላ፣
ሕዝቡ መስመሩን ተከትሎ እየሮጠ ዕልል! ሆ! እያለ ዐጀባቸው።
ጐንደሬዎች እንደዛ ውበት የነገሠበት ሰው አይተው አያውቁምና በምንትዋብ ውበት ተደመሙ። “አቤት መልኳ እንደ ጠሐይ ሚያበራ አቤት ወርቅ አካል!” እያሉ ተደነቁ። በደስታ ተሳክረው ለአፄ ፋሲለደስ፣
አሁን ወጣ ጀንበር
ተደብቆ ነበር
ተብሎ እንደተዘፈነው ሁሉ ለእርሷም፣
አሁን ወጣች ጀንበር
ተሸሽጋ ነበር
እያሉ አዜሙ፤ ጨፈሩ።
አሁን ወጣች ጨረቃ፣
የምትለን ፍርድ ይብቃ።
ደስ ይበልህ ዘመድ፣
ከነገሠች በዘውድ።
ደስ ይበልሽ ወይዘሮ፣
ጭና መጣች ወገሮ።
ደስ ይበልህ ባለእጌ፤
ነገሠች እቴጌ።
ደስ ይበልህ ጐንደር፤
ቀድሞ ከፍቶህ ነበር፣
ሲሉ ጐንደሬዎች ለውዷ ከተማቸው መልካሙን ተመኙላት።
ምንትዋብ የተስፋ ጨረር ፈነጠቀችላቸው።
ዐዲስ ንጉሥ በመጣ ቁጥር የተስፋ ስንቅ ሰንቆ የሚወጣው
መልካሙን ተመኘ ለጦርነት ሳይዳረግ፣ በወታደር ሳይዘረፍ፣ ሚስቱና ልጁ ሳይደፈሩ እኖራለሁ በሚል ተስፋ፣ ከትናንቱ ዛሬ ይሻለኝ ይሆን በሚል ምኞት።
ጐንደሬዎች ምንትዋብን ወደዷት፤ ቀልቧ ገዛቸው፤ መልኳ
አባበላቸው፤ ግርማ ሞገሷ ማረካቸው፣ ኩራታቸው በእሷ ሆነ። በዓለ ንግሥናዋን አደመቁላት፤ ዐደራቸውን ሰጧት፤ ተስፋቸውን ልባቸው ጫፍ ላይ አንጠልጥለው ፎከሩላት፤ ሽለሉላት፤ ዘፈኑላት፤ ጨፈሩላት፤
ዕልል! ሆ! አሉላት።
ጥላዬ፣ ከእነአብርሃ ጋር ከካህናቱ ኋላ ሆኖ አብሮ እየዘመረ ሲሄድ
ድንገት ምንትዋብን ከኢያሱ ጋር አያት። የለበሰችው ነጭ ሐር ቀሚስ፣ፊቷን የጋረደው ነጭ ዐይነርግብ ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዐይኑ ላይ አንፀባረቀበት። ያየውን ሁሉ ማመን አቃተው። የባሏ ለቅሶ ላይ አዝኖላት እንባውን እንደረጨላት ሁሉ አሁን የያዘውን የደስታ ሲቃ መቆጣጠር አቃተው። እንባው ፊቱን አራሰው። እነአብርሃ እንባውን እንዳያዩበት በሰዉ መሃል ተሸለክልኮ ወጥቶ “ኸንግዲህ ደብረ ወርቅ ብመለስም አይቆጨኝ” ብሎ ወደ ቤት ሄደ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ይደልዎ ይደልዎ”
ምንትዋብ፣ ኢያሱ በነገሠ በሁለተኛው ወር ረጅም ነጭ ሐር ቀሚስ ለብሳ፣ በወርቅና በዕንቁ የተንቆጠቆጠ ካባ በላዩ ላይ ደርባ፣ በወርቅ አጊጣ፣ ፊቷን በነጭ ዐይነ ርግብ ከልላ፣ የወርቅ በትረ መንግሥት ጨብጣና ከወርቅ የተሠራ ነጠላ ጫማ ተጫምታ ተሸልማ በወጣችው
በቅሎዋ ላይ ተሰይማ፣ የንግሥ ሥርዐት ወደሚፈጸምበት ወደ መናገሻ ግንብ አመራች።
መናገሻ ግንብ ውስጥ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ አዛዦች፣ ካህናት፣ ሊቃውንትና ወይዛዝርት
እንደየማዕረጋቸው ቦታቸውን ይዘው የንጉሥ መሞት የሚያመጣውን ቀውስ ጠንቅቃ
የምታውቀው ምንትዋብ፣ አክሱም ጽዮን የሚደረገውን ሁለተኛውን
የኢያሱን የንግሥ ሥርዐት አስቀርታ በነገሠ በወሩ ብርሃን ሰገድ የሚል ስመ መንግሥት ከተሰጠው ከዳግማዊ ኢያሱና ከቤተሰቦቿ ጋር ስትገባ ሁሉ ተነሥቶ እጅ ነሳ።
በወርቅ ያጌጠውን የአባቱን ዘውድ የጫነውና የእሳቸውን የወርቅ
በትረ መንግሥት የጨበጠው ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “እናቴን አንግሡልኝ፣ መንግሥቴ ያለሷ አይጠናም” ሲል ተሰብሳቢዎቹ፣ “ይደልዎ ይደልዎ! ይገባታል! ይገባታል! ጎበዝ ክርስቲያን፣ አዋቂ ናት። ሽህ ዓመት ንገሥ። የቆስጦንጢኖስን ምሽት
እሌኒን ትመስላታለች” አሉ።
አንጋሹ ጽራግ ማሰሬ ማሞ ከዕንቁ፣ ከወርቅና ከብር የተሠራውንና በሻሽ ተሸፍኖ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠውን የአፄ ሚናስ የነበረውን ዘውድ አንስተው ምንትዋብ ራስ ላይ ጭነውላት ሲያበቁ ዝቅ ብለው ሰገዱላት፣ ከኢያሱ ቀኝም አስቀመጧት።
ባራኪው እልፍዮስ፣ “እዝጊሃር ክፉዎችን እንዲያሸንፉ ኃይል ይስጥዎ። ክብርዎን ያብዛልዎ። ፈሪሐ እዝጊሃርን በልብዎ ያሳድርልዎ። አቤቱ አምላካችን ሆይ! በአገልጋይህ በእቴጌ ምንትዋብ ላይ እኼን የደስታና
የክብር ዘውድ አኑር፤ እኼውም የቸርነት፣ የርህራሄ፣ የዕውቀትና የጥበብ ዘውድ ይሁንላቸው” ብሎ ሲባርካት፣ ከኋላዋ ቆመው የነበሩት ሴት የመሣፍንት ዘሮችና ወይዛዝርት ዕልልታውን አቀለጡት።
ምንትዋብ ለአምላኳ በልቧ ምስጋና አቀረበች።
ካህናት ዘመሩ፣ ወረቡ፣ ሊቃውንቱ ቅኔ አወረዱ። እንደ ንግሥተ
ሳባ፣ እቴጌ እሌኒ፣ እቴጌ ሰብለወንጌልና እቴጌ መስቀል ክብራን የመሳሰሉ የታላላቅ ሴቶች ስም እየጠቀሱ አሞካሿት። “አንቺ እሌኒ ማለት ነሽ። ልዥሸን ብርሃን ሰገድ ኢያሱን ኸጎኑ ሁነሽ እንደምትረጂው አንጠራጠርም” ሲሉ እሷ ላይ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገለፁላት።
ምንትዋብ፣ አባቷ ዕጣ ፈንታ፣ እናቷ ዕድል አያቷ ግን የተገባት ያሉትን ስትጎናፀፍ ተስተዋለ።
ሕይወት ሲሻት ለጋሥ መሆኗን አስመሰከረች።
ባለ ክራሩና ባለ መሰንቆው የውዳሴና የሙገሳ ግጥም ሲያንቆረቁር፣ፎካሪው በቀረርቶ፣ ሽላዩ በሽለላ የበኩሉን ምስጋና አበረከተ። አንዱ ሀሚና ተነሰቶ በመሰንቆ፣
በወለተጴጥሮስ ተወልዳ በንግርት፣
በእዝጊሄር ፈቃድ በነብያት ትንቢት፤
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ያገራችን ውበት፤
የምታስተባብር ጥድቅ ተሃይማኖት፣
ዳር ድንበር ጠባቂ ያባቶቿን ርስት፣
ኸዝኸ በላይ ጠጋ ኻአምላክ መሰጠት፣
ምንድን ሊሰጧት ነው ምንትዋብ ሚሏት?
እያለ ሲያሞግሳት፣ የተሰበሰበው ሰው ደግሞ እሱን አመሰገነው።
ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መለከት እየተነፋ ከመናገሻ ግንብ በደጅ
አጋፋሪው አቀናባሪነት የፊቱን ወጀብ ሰንደቅ የያዙ፣ የእልፍኝ አሽከሮች፣ባለሟሎችና ሠይፈ ጃግሬዎች ፈንጠር ብለው እየመሩ፣ የመሃል ዐጀቡ
በእልፍኝ አስከልካዩ እየተጠበቀ፣ ኢያሱና ምንትዋብ ጎን ለጎን ሆነው
ድባብ ተይዞላቸው፣ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ ሊቃውንት፣ ወይዛዝርት፣ግራዝማቾች፣ ቀኛዝማቾችና የጦር አበጋዞች እንደየደረጃቸው ከኋላ
እያጀቧቸው፣ ሰልፍ አስከባሪዎቹና የንጉሠ ነገሥቱ ጠባቂ የሆኑት ጋሻዐጃግሬዎቹ ተከትለው የሰልፉን ግራና ቀኝ አንጋቾች እየጠበቁ ራስ ቢትወደዱ በመጨረሻ ተሰልፈው ነገሥታቱ በዘፈንና በጭፈራ ከግቢ
ሲወጡ ካህናት፣
መንክር ግርማ መንክር ግርማ
ወልደልዑል ጸለላ መንክር ግርማ
የምትደንቅ ግርማ ሞገስን
የምትደንቅ ግርማ ሞገስ
የወልደልዑል ልጅ፣ እጅግ የላቀው አባት ልጅ፤
እያሉ፣ ምንትዋብ በወንድሟ በወልደልዑል መከታነት መንገሧን
በቅኔ ጠቅ እያደረጉ በፀናፅልና በከበሮ ዐጀቧት።
ዘውዷን እንደጫነች በቅሎዋ ላይ ተሰይማና ታጅባ፣ ወደ ሕዝቡ
አመራች። ከጐንደርና ከአካባቢዋ የመጣው ነፍጠኛ፣ ገበሬ፣ እረኛ፣
ነጋዴ፣ ወታደር፣ አንጥረኛ፣ ሸማኔ፣ ቆዳ አልፊ፣ ጥልፍ ጠላፊ፣ ሹሩባ ሠሪ መድኃኒት አዋቂ፣ ወጌሻ፣ የቤት እመቤት፣ አረቄና ጠላ ሻጭ፣ ዲያቆን ተማሪ ፣ የቁም ጸሐፊ፣ ሠዓሊ፣ ብራና ሠሪ፣ ባለክራሩና ባለመሰንቆው
ሴቱ ሹሩባውን አንዠርጎ፣ ነጠላውን አጣፍቶ፣ ወገቡን በድግ ደግፎ ማተቡ ላይ የእንጨት መስቀሉን፣ ድሪውን፣ ጨሌውን፣ ዶቃውን ቁርጭምጭሚቱ ዙርያ አልቦውን፣ የእጁ አንጓ ላይ አንባሩን ደርድሮ ገሚሱ የቀርከሀ ጃንጥላውን አጥልቶ፣ ወንዱ ፀጉሩን አጎፍሮ፣ ለምዱን ደርቦ፣ ዱላውን ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ፣ ልጆች ጥብቋቸውን
አጥልቀው፣ ክታባቸውን አንጠልጥለው ምንትዋብ ከኢያሱ ጋር ጃን ተከል ብቅ ስትል አካባቢው ድብልቅልቁ ወጣ።
ሴቶች በዕልልታና በእስክስታ፣ ወንዶች በሆታና በጭፈራ አካባቢውን አናጉት፤ ካህናት በሽብሸባ አደመቁት። እነምንትዋብ ካለፉ በኋላ፣
ሕዝቡ መስመሩን ተከትሎ እየሮጠ ዕልል! ሆ! እያለ ዐጀባቸው።
ጐንደሬዎች እንደዛ ውበት የነገሠበት ሰው አይተው አያውቁምና በምንትዋብ ውበት ተደመሙ። “አቤት መልኳ እንደ ጠሐይ ሚያበራ አቤት ወርቅ አካል!” እያሉ ተደነቁ። በደስታ ተሳክረው ለአፄ ፋሲለደስ፣
አሁን ወጣ ጀንበር
ተደብቆ ነበር
ተብሎ እንደተዘፈነው ሁሉ ለእርሷም፣
አሁን ወጣች ጀንበር
ተሸሽጋ ነበር
እያሉ አዜሙ፤ ጨፈሩ።
አሁን ወጣች ጨረቃ፣
የምትለን ፍርድ ይብቃ።
ደስ ይበልህ ዘመድ፣
ከነገሠች በዘውድ።
ደስ ይበልሽ ወይዘሮ፣
ጭና መጣች ወገሮ።
ደስ ይበልህ ባለእጌ፤
ነገሠች እቴጌ።
ደስ ይበልህ ጐንደር፤
ቀድሞ ከፍቶህ ነበር፣
ሲሉ ጐንደሬዎች ለውዷ ከተማቸው መልካሙን ተመኙላት።
ምንትዋብ የተስፋ ጨረር ፈነጠቀችላቸው።
ዐዲስ ንጉሥ በመጣ ቁጥር የተስፋ ስንቅ ሰንቆ የሚወጣው
መልካሙን ተመኘ ለጦርነት ሳይዳረግ፣ በወታደር ሳይዘረፍ፣ ሚስቱና ልጁ ሳይደፈሩ እኖራለሁ በሚል ተስፋ፣ ከትናንቱ ዛሬ ይሻለኝ ይሆን በሚል ምኞት።
ጐንደሬዎች ምንትዋብን ወደዷት፤ ቀልቧ ገዛቸው፤ መልኳ
አባበላቸው፤ ግርማ ሞገሷ ማረካቸው፣ ኩራታቸው በእሷ ሆነ። በዓለ ንግሥናዋን አደመቁላት፤ ዐደራቸውን ሰጧት፤ ተስፋቸውን ልባቸው ጫፍ ላይ አንጠልጥለው ፎከሩላት፤ ሽለሉላት፤ ዘፈኑላት፤ ጨፈሩላት፤
ዕልል! ሆ! አሉላት።
ጥላዬ፣ ከእነአብርሃ ጋር ከካህናቱ ኋላ ሆኖ አብሮ እየዘመረ ሲሄድ
ድንገት ምንትዋብን ከኢያሱ ጋር አያት። የለበሰችው ነጭ ሐር ቀሚስ፣ፊቷን የጋረደው ነጭ ዐይነርግብ ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዐይኑ ላይ አንፀባረቀበት። ያየውን ሁሉ ማመን አቃተው። የባሏ ለቅሶ ላይ አዝኖላት እንባውን እንደረጨላት ሁሉ አሁን የያዘውን የደስታ ሲቃ መቆጣጠር አቃተው። እንባው ፊቱን አራሰው። እነአብርሃ እንባውን እንዳያዩበት በሰዉ መሃል ተሸለክልኮ ወጥቶ “ኸንግዲህ ደብረ ወርቅ ብመለስም አይቆጨኝ” ብሎ ወደ ቤት ሄደ።
👍16
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
"በእግዝሃር ፍጥረት ሴት ልሁን እንጂ ምን ይጎለኛል?”
ምንትዋብ ለራሷ፣ ለሃገሯና ለጐንደር በገባችው ቃል መሠረት
በቅድሚያ ሰላም ማስፈንንና ሃገር ማረጋጋትን መረጠች። ለዚህም
እንዲበጅና የልጇን መንግሥት ለማደላደልና ለማጠናከር ንጉሥ
ሲነግሥ እንደሚደረገው ከብርሃን ሰገድ ኢያሱ ጋር ሆና መኳንንቱን
አሸዋ ግንብ ሰብስባ ሹመት ሰጠች። ሕዝቡ የወደደውን ሹመቱ እንዲጸና አደረገች፤ የሚሻረውን ሻረች።
የልጇን መንግሥት ይበልጥ ለማጠናከር ግራዝማች ኒቆላዎስን፣ አዛዥ አርከሌድስንና ወልደልዑልን ደጃዝማች ብላ ሾመቻቸው።
በደንቡ መሠረት ግብር አገባች፣ ብላም ከመኳንንቱ ጋር ምክክር
አደረገች።በምክክሩ መሠረት ደጃዝማች ኮንቤን የጃዊና የዳሞት ገዢ ኣድርጋ በመሾሟ ቀድሞውንም አፄ በካፋ ላይ ሲያምጹ የነበሩት ጃዊዎች
ኮንቤን አንፈልግም ሲሉ እሷም ላይ አመጹባት። ለምን ሹመቱን
እንደተቃወሙ ስትጠይቅ፣ “ኸራሳችን የወጣ፣ ወግ ልማዳችንን ሚያቅ ኸራሳችን የተወለደ ይሾምልን” አሏት።
መኳንንቱን እንደገና ወርቅ ሰቀላ ውስጥ ሰብስባ መከረች።
መጽሐፉም ወኩሎ በዘትገብር ተማከር ምስለ ሰብእ፡ እስመ ዘእንበለ ምክርሰ ገቢር ዕበድ ውእቱ ማንኛውንም ስራ ስትሠራ ከሰዎች ጋር ተማከር፤ አለበለዚያ የሰነፍ ሥራ ይሆንብሀል ነው የሚለው።
መኳንንቱም፣ “እንደ ልማዳቸው እናርግላቸው” አሉ። ምንትዋብ
ተቀበለች። ሻለቃ ወረኛን ብትልክላቸው ጃዊዎች ፈነጠዙ፤ ተረጋጉ።እሷም የመጀመሪያውን የአስተዳደር ትምህርት ገበየች። እንደገናም ከኢያሱ ጋር ሆና ሃገር ላረጋጉት ሹመት ሰጠች።
ሕዝቡን አስደስታ፣ እሷም ተደሰተች፣ ሃገርም ተረጋጋች:
ደስታውና መረጋጋቱ ግን በአስተዳደር በኩል ሊገጥማት ከሚችለው ችግር ለረጅም ጊዜ ሊያድናት አለመቻሉን በመገንዘብ፣ ከመኳንንቱ ጋር ከምታደርገው ምክክር ውጭ ብዙውን ጊዜዋን ከኒቆላዎስ፣ከወልደልዑል፣ ከአርከሌድስ፣ ከአያቷ፣ ከእናቷ፣ ከአጎቷና ከአጎቷ ልጆች
ጋር እየተሰበሰበች ስለአስተዳደር መወያየትን ልማድ አደረገች።
እንደሁልጊዜያቸው አንድ ቀን እልፍኝ ውስጥ ተሰብስበው ሳለ፣
“እኔ ስንኳ” አለቻቸው። “እኔ ስንኳ ሌት ተቀን ማስበው እንዴት
ላስተዳድር እያልሁ ነው። የነገሥሁ ዕለት ድኻው ምንኛ ተስፋ
እንደጣለብኝ አይቻለሁ። ኸነሱ ተስፋ አንሼ ልገኝ አልሻም። ምኞቴ
ሁሉ ላገሬ መልካም ማረግ ነው። ሌላው ደሞ ኸመኳንንቱ መኻልም
ቋረኛ ሊገዛን?'፣ ብሎ ብሎ ቋረኛ ይንገሥ?” ሚሉ እንዳሉ አውቃለሁ።ቋረኛ ብሆን ኸነሱ እንደማላንስ ማሳየት ፈልጋለሁ። በናንተ ድጋፍ መዠመሪያ መጠናከር አለብኝ። እኔ ዋናው አገር እንዲረጋጋና የኢያሱ
አልጋ እንዲደላደል ነው ምፈልግ። የኢያሱ አልጋ እንዲደላደል ደሞ
አገር መረጋጋት አለበት።”
እንደ ባሏ የግዛት ዘመኗን አመጽ እያበረዱ ማሳለፍ አልፈቀደችም።
ይህን ስታሰላስል ወልደልዑል ሲናገር፣ ከእንቅልፏ እንደባነነች ሁሉ ራሷን ነቅነቅ ዐይኗን እርግብግብ እያደረገች አየችው።
ስሜቷን ተረድቶ ሐሳቧንም እንደሚጋራ ሊያሳያት፣ “ምታስቢው ሁሉ ይገባኛል” አላት። “ልክ ነው። ድኻው ተስፋውን ኻንቺ አኑሯልና
ቢከብድሽ አያስገርምም። ሁሉን እንደምትወጪ ግን እንተማመንብሻለን።
እንዳልሽውም ደሞ ኸቋራ ስለመጣሽ ንቀትና ጥርጣሬ አላቸው። ቋረኛ የፍየልም እረኛ ማዶል ሚሉን? ቋራን እንደዝኸ ንቀው እኼው አንቺን አፈራ። አንቺም ደሞ ማን እንደ ሆንሽ ማሳየት አለብሽ። እንዳው ነው እንጂ ኸየትም ነይ ኸየትም ሥራሽ ነው ሚያስመሰግንሽ። አሁንም
ጠንክረሽ ማስተዳደር ነው ያለብሽ። እንዳልሽው የአጤ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ አልጋ እንዲደላደል አገር መረጋጋት አለበት። አገር እንዲረጋጋ
ደሞ አንዱ ኸመኳንንቱ ጋር ስምም መሆን ነው። እነሱ ማዶሉ ለሰዉ ሚቀርቡ? ኻለነሱ የት ይሆናል ። ባለፈው የዳሞት ገዢ የነበረው ተንሴ ማሞ ብዙ ግዝየ፣ “እኒህ ቋረኞች” ሲል ተሰምቷል ። ግዝየውን ጠብቆ ማመጡ አይቀርም። ወህኒ አምባን ደሞ በሚገባ ማስጠበቅ አለብን።
እኔም ሁሉን ባይነቁራኛ እመለከታለሁ” አለና እነአርከሌድስን መልከት
አድርጎ፣ “እኛ እስታለን ድረስ ጥቃት አይደርስብሽም። አንቺም
በተፈጥሮሽ ጠንካራና አስተዋይ ነሽ” አላት።
“ላለፉት ሰባት ዓመታት ስለቤተመንግሥት ብዙ ነገር ተምሬያለሁ”አለቻቸው፣ እጆቿን ደረቷ ላይ አስቀምጣ። “እኼ ይመጣል ብየም ባይሆን ማን ምን እንደ ሆነ ሳጠና ነው የቆየሁ። ቋራ ሳለሁ እንዳው ንጉሥ አዛዥ ናዛዥ ይመስለኝ ነበር...”
ኒቆላዎስ ጣልቃ ገባ፣ “ንጉሥ በርግጥም አዛዥ ናዛዥ ነው። መኳንንቱ ብዙውን ግዝየ ኸንጉሡ በዝምድናም ይሁን በጋብቻ የተሳሰሩ ቢሆኑም ንጉሡ የፈለጉትን መኰንን በፈለጉ ግዘየ ያለ ማስጠንቀቂያ ኸማረጉ
ሊያነሱት፣ ይዞታውን ሁሉ ሊነጥቁት ይችላሉ። አይተሽ የለ እንዴ አንድ መኰንን ያለ ንጉሡ ፈቃድ መዘዋወር ስንኳ እንደማይችል? ግና ያለ መኳንንቱ መንግሥት አይጠናም። አማካሮቹ፣ የቤተመንግሥት
ምሰሶዎቹ እነሱኮ ናቸው። እነሱን በጅ ማረግና ኸነሱ መምከር ግዴታ ነው። ፍታ ነገሥቱም ያዛል። ፈላስፋውም ቢሆን 'በገዛ ራሱ ምክር ብቻ ሚኸድ ሰው ይደክመዋል፣ ኻልሆነም ነገር ወድቆ ይቀራል ይል የለ?
ደሞስ ግብር ሰብሳቢዎቹ፣ ጦርነት ሲኖር ተዋጊዎቹና አዋጊዎቹ እነሱ
ማዶሉ? ፍርድ ሸንጎ ሚቀመጡ፣ ዳኛ ሚሆኑም እነሱ ናቸው። ንጉሡ ነው ሚፈርዱ። የግዛቶቹ ሁሉ አስተዳዳሪዎችም እነሱው ናቸው። አንድ ሲፈልጉ የራሳቸውን ፍርድ ቢሰጡም፣ የነሱን ሰምተውና አመዛዝነው
መኰንን አመጸብሽ ማለት አንድ ግዛት ይዞብሽ ኸደ ማለት ነው።
ያኔ ለማስገበር ጦርነት ትገጥሚያለሽ። በመጨረሻም ኸወህኒ አንዱን አምጥተው ያነግሡብሻል።ኻንች ከሆኑ አመጥ ቢነሳ ስንኳ ሚያዳፍኑልሽ
እነሱም ናቸው። ሚያቀጣጥሉብሽም እነሱ ሊሆኑ ይችላሉ። ስለዝኸ አብረሽ እየመከርሽ፣ እየሾምሽና እየሸለምሽ ይዞታቸውን እየጠበቅሽና እየጨመርሽ ነው መያዝ ያለብሽ። እንካ በእንካ ነው ነገሩ። ስትሾሚ ደሞ ባለፈው እንዳረግሽው ጥሩ ሚያስተዳድረውን ትሾሚያለሽ፤
ማይጠቅመውን ታማኝ ቢሆንም ስንኳ ትሽሪያለሽ።”
“እኔ አሳቤ ያው ጃንሆይ እንደሚያረጉት ኸጥንትም ቢሆን ያለ ማዶል? የመኻሉን ጠበቅ አርጌ ይዤ የሩቁን ግዛታቸውን እንደ ልማዳቸው ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ነው.. ያው አሁን ለጃዊዎች እንዳረግነው። ዋናው ዓላማየ አገር ማረጋጋትና መንግሥት ማደላደልነው።”
“አንገብርም ብለው ኻላመጡና ድኻውን ኻልበደሉ በቀር ጣልቃ
ሳትገቢ” አላት፣ ኒቆላዎስ።
“አዎ ጣልቃ ሳልገባባቸው። መኳንንቱ ብዙ ግዝየ ኸዝኸ ይመጡ የለ? ቤታቸው ራሱ እዝሁ ቤተመንግሥት አጠገብ ነው። ምማከረውም ኸነሱ ነው። ማነንም ጦር እያነሱ ማስገበር አልፈልግም። በሰላም አንድ
ሁነን እነሱም ግብር እያገቡ፣ ድኻውን በደንቡ እያስተዳደሩ መኖርን ነው ምመርጥ። እነሱም ሆኑ ድኻው እኔ ላይ እምነት እንዲጥሉ ፈቃዴ ነው። እምነት ኻልጣሉብኝ እንዴት ማስተዳደር እችላለሁ? ጥሩ ታስተዳደርሁ ደሞ እምነት እንደሚጥሉብኝ አውቃለሁ።”
“ትክክል” አሉ፣ ዮልያና።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
"በእግዝሃር ፍጥረት ሴት ልሁን እንጂ ምን ይጎለኛል?”
ምንትዋብ ለራሷ፣ ለሃገሯና ለጐንደር በገባችው ቃል መሠረት
በቅድሚያ ሰላም ማስፈንንና ሃገር ማረጋጋትን መረጠች። ለዚህም
እንዲበጅና የልጇን መንግሥት ለማደላደልና ለማጠናከር ንጉሥ
ሲነግሥ እንደሚደረገው ከብርሃን ሰገድ ኢያሱ ጋር ሆና መኳንንቱን
አሸዋ ግንብ ሰብስባ ሹመት ሰጠች። ሕዝቡ የወደደውን ሹመቱ እንዲጸና አደረገች፤ የሚሻረውን ሻረች።
የልጇን መንግሥት ይበልጥ ለማጠናከር ግራዝማች ኒቆላዎስን፣ አዛዥ አርከሌድስንና ወልደልዑልን ደጃዝማች ብላ ሾመቻቸው።
በደንቡ መሠረት ግብር አገባች፣ ብላም ከመኳንንቱ ጋር ምክክር
አደረገች።በምክክሩ መሠረት ደጃዝማች ኮንቤን የጃዊና የዳሞት ገዢ ኣድርጋ በመሾሟ ቀድሞውንም አፄ በካፋ ላይ ሲያምጹ የነበሩት ጃዊዎች
ኮንቤን አንፈልግም ሲሉ እሷም ላይ አመጹባት። ለምን ሹመቱን
እንደተቃወሙ ስትጠይቅ፣ “ኸራሳችን የወጣ፣ ወግ ልማዳችንን ሚያቅ ኸራሳችን የተወለደ ይሾምልን” አሏት።
መኳንንቱን እንደገና ወርቅ ሰቀላ ውስጥ ሰብስባ መከረች።
መጽሐፉም ወኩሎ በዘትገብር ተማከር ምስለ ሰብእ፡ እስመ ዘእንበለ ምክርሰ ገቢር ዕበድ ውእቱ ማንኛውንም ስራ ስትሠራ ከሰዎች ጋር ተማከር፤ አለበለዚያ የሰነፍ ሥራ ይሆንብሀል ነው የሚለው።
መኳንንቱም፣ “እንደ ልማዳቸው እናርግላቸው” አሉ። ምንትዋብ
ተቀበለች። ሻለቃ ወረኛን ብትልክላቸው ጃዊዎች ፈነጠዙ፤ ተረጋጉ።እሷም የመጀመሪያውን የአስተዳደር ትምህርት ገበየች። እንደገናም ከኢያሱ ጋር ሆና ሃገር ላረጋጉት ሹመት ሰጠች።
ሕዝቡን አስደስታ፣ እሷም ተደሰተች፣ ሃገርም ተረጋጋች:
ደስታውና መረጋጋቱ ግን በአስተዳደር በኩል ሊገጥማት ከሚችለው ችግር ለረጅም ጊዜ ሊያድናት አለመቻሉን በመገንዘብ፣ ከመኳንንቱ ጋር ከምታደርገው ምክክር ውጭ ብዙውን ጊዜዋን ከኒቆላዎስ፣ከወልደልዑል፣ ከአርከሌድስ፣ ከአያቷ፣ ከእናቷ፣ ከአጎቷና ከአጎቷ ልጆች
ጋር እየተሰበሰበች ስለአስተዳደር መወያየትን ልማድ አደረገች።
እንደሁልጊዜያቸው አንድ ቀን እልፍኝ ውስጥ ተሰብስበው ሳለ፣
“እኔ ስንኳ” አለቻቸው። “እኔ ስንኳ ሌት ተቀን ማስበው እንዴት
ላስተዳድር እያልሁ ነው። የነገሥሁ ዕለት ድኻው ምንኛ ተስፋ
እንደጣለብኝ አይቻለሁ። ኸነሱ ተስፋ አንሼ ልገኝ አልሻም። ምኞቴ
ሁሉ ላገሬ መልካም ማረግ ነው። ሌላው ደሞ ኸመኳንንቱ መኻልም
ቋረኛ ሊገዛን?'፣ ብሎ ብሎ ቋረኛ ይንገሥ?” ሚሉ እንዳሉ አውቃለሁ።ቋረኛ ብሆን ኸነሱ እንደማላንስ ማሳየት ፈልጋለሁ። በናንተ ድጋፍ መዠመሪያ መጠናከር አለብኝ። እኔ ዋናው አገር እንዲረጋጋና የኢያሱ
አልጋ እንዲደላደል ነው ምፈልግ። የኢያሱ አልጋ እንዲደላደል ደሞ
አገር መረጋጋት አለበት።”
እንደ ባሏ የግዛት ዘመኗን አመጽ እያበረዱ ማሳለፍ አልፈቀደችም።
ይህን ስታሰላስል ወልደልዑል ሲናገር፣ ከእንቅልፏ እንደባነነች ሁሉ ራሷን ነቅነቅ ዐይኗን እርግብግብ እያደረገች አየችው።
ስሜቷን ተረድቶ ሐሳቧንም እንደሚጋራ ሊያሳያት፣ “ምታስቢው ሁሉ ይገባኛል” አላት። “ልክ ነው። ድኻው ተስፋውን ኻንቺ አኑሯልና
ቢከብድሽ አያስገርምም። ሁሉን እንደምትወጪ ግን እንተማመንብሻለን።
እንዳልሽውም ደሞ ኸቋራ ስለመጣሽ ንቀትና ጥርጣሬ አላቸው። ቋረኛ የፍየልም እረኛ ማዶል ሚሉን? ቋራን እንደዝኸ ንቀው እኼው አንቺን አፈራ። አንቺም ደሞ ማን እንደ ሆንሽ ማሳየት አለብሽ። እንዳው ነው እንጂ ኸየትም ነይ ኸየትም ሥራሽ ነው ሚያስመሰግንሽ። አሁንም
ጠንክረሽ ማስተዳደር ነው ያለብሽ። እንዳልሽው የአጤ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ አልጋ እንዲደላደል አገር መረጋጋት አለበት። አገር እንዲረጋጋ
ደሞ አንዱ ኸመኳንንቱ ጋር ስምም መሆን ነው። እነሱ ማዶሉ ለሰዉ ሚቀርቡ? ኻለነሱ የት ይሆናል ። ባለፈው የዳሞት ገዢ የነበረው ተንሴ ማሞ ብዙ ግዝየ፣ “እኒህ ቋረኞች” ሲል ተሰምቷል ። ግዝየውን ጠብቆ ማመጡ አይቀርም። ወህኒ አምባን ደሞ በሚገባ ማስጠበቅ አለብን።
እኔም ሁሉን ባይነቁራኛ እመለከታለሁ” አለና እነአርከሌድስን መልከት
አድርጎ፣ “እኛ እስታለን ድረስ ጥቃት አይደርስብሽም። አንቺም
በተፈጥሮሽ ጠንካራና አስተዋይ ነሽ” አላት።
“ላለፉት ሰባት ዓመታት ስለቤተመንግሥት ብዙ ነገር ተምሬያለሁ”አለቻቸው፣ እጆቿን ደረቷ ላይ አስቀምጣ። “እኼ ይመጣል ብየም ባይሆን ማን ምን እንደ ሆነ ሳጠና ነው የቆየሁ። ቋራ ሳለሁ እንዳው ንጉሥ አዛዥ ናዛዥ ይመስለኝ ነበር...”
ኒቆላዎስ ጣልቃ ገባ፣ “ንጉሥ በርግጥም አዛዥ ናዛዥ ነው። መኳንንቱ ብዙውን ግዝየ ኸንጉሡ በዝምድናም ይሁን በጋብቻ የተሳሰሩ ቢሆኑም ንጉሡ የፈለጉትን መኰንን በፈለጉ ግዘየ ያለ ማስጠንቀቂያ ኸማረጉ
ሊያነሱት፣ ይዞታውን ሁሉ ሊነጥቁት ይችላሉ። አይተሽ የለ እንዴ አንድ መኰንን ያለ ንጉሡ ፈቃድ መዘዋወር ስንኳ እንደማይችል? ግና ያለ መኳንንቱ መንግሥት አይጠናም። አማካሮቹ፣ የቤተመንግሥት
ምሰሶዎቹ እነሱኮ ናቸው። እነሱን በጅ ማረግና ኸነሱ መምከር ግዴታ ነው። ፍታ ነገሥቱም ያዛል። ፈላስፋውም ቢሆን 'በገዛ ራሱ ምክር ብቻ ሚኸድ ሰው ይደክመዋል፣ ኻልሆነም ነገር ወድቆ ይቀራል ይል የለ?
ደሞስ ግብር ሰብሳቢዎቹ፣ ጦርነት ሲኖር ተዋጊዎቹና አዋጊዎቹ እነሱ
ማዶሉ? ፍርድ ሸንጎ ሚቀመጡ፣ ዳኛ ሚሆኑም እነሱ ናቸው። ንጉሡ ነው ሚፈርዱ። የግዛቶቹ ሁሉ አስተዳዳሪዎችም እነሱው ናቸው። አንድ ሲፈልጉ የራሳቸውን ፍርድ ቢሰጡም፣ የነሱን ሰምተውና አመዛዝነው
መኰንን አመጸብሽ ማለት አንድ ግዛት ይዞብሽ ኸደ ማለት ነው።
ያኔ ለማስገበር ጦርነት ትገጥሚያለሽ። በመጨረሻም ኸወህኒ አንዱን አምጥተው ያነግሡብሻል።ኻንች ከሆኑ አመጥ ቢነሳ ስንኳ ሚያዳፍኑልሽ
እነሱም ናቸው። ሚያቀጣጥሉብሽም እነሱ ሊሆኑ ይችላሉ። ስለዝኸ አብረሽ እየመከርሽ፣ እየሾምሽና እየሸለምሽ ይዞታቸውን እየጠበቅሽና እየጨመርሽ ነው መያዝ ያለብሽ። እንካ በእንካ ነው ነገሩ። ስትሾሚ ደሞ ባለፈው እንዳረግሽው ጥሩ ሚያስተዳድረውን ትሾሚያለሽ፤
ማይጠቅመውን ታማኝ ቢሆንም ስንኳ ትሽሪያለሽ።”
“እኔ አሳቤ ያው ጃንሆይ እንደሚያረጉት ኸጥንትም ቢሆን ያለ ማዶል? የመኻሉን ጠበቅ አርጌ ይዤ የሩቁን ግዛታቸውን እንደ ልማዳቸው ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ነው.. ያው አሁን ለጃዊዎች እንዳረግነው። ዋናው ዓላማየ አገር ማረጋጋትና መንግሥት ማደላደልነው።”
“አንገብርም ብለው ኻላመጡና ድኻውን ኻልበደሉ በቀር ጣልቃ
ሳትገቢ” አላት፣ ኒቆላዎስ።
“አዎ ጣልቃ ሳልገባባቸው። መኳንንቱ ብዙ ግዝየ ኸዝኸ ይመጡ የለ? ቤታቸው ራሱ እዝሁ ቤተመንግሥት አጠገብ ነው። ምማከረውም ኸነሱ ነው። ማነንም ጦር እያነሱ ማስገበር አልፈልግም። በሰላም አንድ
ሁነን እነሱም ግብር እያገቡ፣ ድኻውን በደንቡ እያስተዳደሩ መኖርን ነው ምመርጥ። እነሱም ሆኑ ድኻው እኔ ላይ እምነት እንዲጥሉ ፈቃዴ ነው። እምነት ኻልጣሉብኝ እንዴት ማስተዳደር እችላለሁ? ጥሩ ታስተዳደርሁ ደሞ እምነት እንደሚጥሉብኝ አውቃለሁ።”
“ትክክል” አሉ፣ ዮልያና።
👍5
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...ከራስ ቢትወደድ ዘጊዮርጊስ መሸነፍ በኋላ፣ ሰላም ቀስ በቀስ በሃገሪቱ መልሶ ሰፈነ። ምንትዋብ በነገሠች በዓመቱ እንደ ቀድሞ ነገሥታት የራሷ የሆነ ቤተመንግሥት ለማሠራት ያደረባትን ጽኑ ፍቅርና ፍላጎት
ለማርካት ከባለቤቷ ከአፄ በካፋ ግንብ ጎን ቆማ ያሠራችው የተዋበውና የረቀቀው ፣ እንደ ሌሎቹ ግንቦች ሁሉ ባለ ሰቀሰቁና ባለ ሁለት ደርቡ ቤተመንግሥት የተደነቀ ሆነላት።
አፄ በካፋ በሞቱ በሁለተኛ ዓመታቸው ላይ ያሳደጓት፣ ያስተማሯት፣ በቤተመንግሥት ሥርዐት ሆነ በአስተዳደር ታንጻ እንድትወጣ የረዷት፣ አንደበተ ርቱዕዋ፣ የቤተክህነት ትምህርትና የቤተመንግሥት ወግ አዋቂዋ አያቷ ወይዘሮ ዮልያና ይህችን ምድር ጥለው ሄዱ። እሷ
ሆነች እናቷ መሪር ሐዘን ገባቸው። ዮልያና ታላቅ የቀብር ሥርዐት
ተደርጎላቸው ተቀባሩ። ምንትዋብ ተዝካራቸውንም ታላቅ ድግስ ደግሳ አወጣች።
ዮልያና በሞቱ በስድስተኛ ወራቸው ታናሽ ወንድማቸው ኒቆላዎስ ዐረፈ። ምንትዋብ ተጎዳች። ሆኖም ኒቆላዎስ በታላቅ ለቅሶና ሐዘን ተገቢው ሥርዐት ተደርጎለት ተቀበረ። ቀድሞውንም ቢሆን ለአፄ በካፋ ሁነኛ የነበረና በኋላም፣ ከእሷ ቀጥሎ ትልቁ ባለሥልጣን የነበረ፣አጋሯና በማንኛውም መንገድ ሲያግዛት፣ ሲያማክራትና ትዕዛዞቿን ሁሉ በተገቢው መንገድ ሲያስፈጽምላትና ሲፈጽምላት የቆየ ቀኝ እጇ በመሆኑ፣ የእሱ መሞት በቤተመንግሥት ውስጥ ትልቅ ክፍተት ፈጠረ።
ኒቆላዎስ ከሞተ ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ ምንትዋብና ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ዐዲሱ ቤተመንግሥት እልፍኝ ውስጥ እጅ የሚነሱትን መሣፍንትና መኳንንት አሰናብተው ጨርሰው፣ ኢያሱ ከአጃቢዎቹ ጋር ወጥቷል።
ምንትዋብም እልፍኟ ለመግባት ዝግጅት ላይ ነች፡፡ ደጃዝማች
ወልደልዑል ጫማውን ሳያወልቅ እልፍኝ ዘው ሲል ከአረማመዱ የሆነ ነገር እንደገጠመው አወቀች። ዛሬ ወልድየ ምንን ሁኖ ነው አለወትሮው በችኮላ ሚራመደው አለች፣ ትኩር ብላ እያየችው።
“ችግር አለ” አላት፣ የችኮላ ሰላምታ ከሰጣት በኋላ።
“የምን ችግር ወልድየ?” ከተቀመጠችበት ተነሳች።
“የጃንሆይ መኰንን የነበረው ተንሴ ማሞ ለውጊያ ታጥቋል።”
“ምን ይሁን ብሎ?” ፊቷ ጥላ ጣለበት። “ምን ይሁን ብሎ ነው አሁን ጦር ይዞ ሚነሳ?”
“ኸኢያሱ ክፍል የለኝም ብሎ። ያው ፊት እንደሰማነው፣ እኒህ
ቋረኞች እስተመቸ ነው ሚገዙን ብሎ።”
ከቋራ ስለመምጣቷ ከአያቷ ጋር ሲያወሩ፣ “ንቀታቸው... ወደ ፊት
ታቂዋለሽ” ያሉት ትዝ አላትና ራሷን በትዝብት ነቀነቀች። “እኒህ
ቋረኞች እስተመቸ ነው ሚገዙን ብሎ?” አለችና ከት ብላ የምጸት ሳቅ ሳቀች።
“አዎ እስተመቸ ነው ሚገዙን እያለ ሲቆጭ ቆይቷል” አላትና
እንድትቀመጥ በእጁ ዙፋኗን አመለከታት።
ቀጥል በሚል እጇን አወዛወዘችለት።
“አንዱም ኸተሰጠው የዳሞት ገዥነት ስለወረደ በልቡ ቂም ኣሳድሮ ነው እኼን ሊያረግ የተነሳው። ጥላቻውና እብሪቱ መጠን አጥቶ እዋጋለሁ ብሎ ነገሩን ኻዘጋጀ ሰንብቷል። “
እኼን የኩበት ካብ ሳላፈርስ
ሰው አልባልም ብሏል አሉ።”
“የኩበት ካብ?”
“የንጉሥ ኢያሱንና ያንቺን መንግሥት ማለቱ ነዋ!”
“ዛዲያማ ይጠብቀና” አለች፣ ሌባ ጣቷን እያወዛወዘች።
“ኸመጣሽ ዠምሮ ቋረኞች ላይ ያለው ግምት ምን እንደሁ
ታውቂያለሽ። አንቺም ብትሆኚ አልተሸነፍሽላቸውም፤ ወደፊትም
ታሸንፊያቸዋለሽ። ስሰማ ተንሴ ማሞ ኸዝኸ ሁሉ መጥቶ ግቢውን
አይቶ ነው አሉ የኸደው። ተመልሸ መጣለሁ ብሎ ዝቷል።”
“እንዴት ልቡ አብጧል በል? ይምጣ... ይምጣ... እስቲ እናያለን
የኩበት ካቡን ሲያፈርስ። የልዢን አልጋ ኻላስከበርሁማ እኔ ምንትዋብ ሰው ማዶለሁ” አለች።
ሰውነቷ ጋለ።
“አሳቡ አንቺንና ንጉሥ ኢያሱን መግደል ነው። መንገስ ሚፈልገውን ጠይቆ ሊመጣ ወህኒ ኸዷል። ወንድሙ ተስፋ ማሞም
ኸሱ ጋር አምጿል። ኸጎዣምም ብዙ ሠራዊት ሰብስቧል አሉ። እኛም መዘጋጀት አለብን።”
ለጥቂት ጊዜ ዝም ብላ አየችውና፣ “ሚነግሠውን ያምጣ። የትኛው
አልጋ ላይ እንደሚያስቀምጠው እናያለን። ይልቅስ አሁን ኸመሣፍንቱ፣ ኸመኳንንቱና ኸጦር አበጋዞቹ ጋር እንምከር። ለወሎና ለጎዣም ባላባትም ስለሁኔታው እናመላክታቸው። ዛሬውኑ መልክተኛ እንላክ።ጠንካራ ጦር ስላላቸው ኸነሱ ጋር ተባብረን ነው እኒህን ሰዎች መቋቋም
ምንችለው። ዛሬውኑ ሁነኛ ሰው ላክና እንዲደርሱልን አርግ::”
“በጀ፤ እንደሱ አረጋለሁ” ብሏት እጅ ነስቶ ወጣ።
የእልፍኝ አስከልካዩን ቴዎድሮስን አስጠራች።መኳንንቱና የጦር አበጋዞቹ በአስቸኳይ መሠሪ
እንዲነግራቸው ነገረችው። ኢያሱም ከግቢ እንዳይወጣ ትዕዛዝ ሰጠች።ቴዎድሮስ እጅ ነስቶ በፍጥነት ወጣ።
ዙፋኗ ላይ ተቀመጠች። “የጃንሆይ መኰንን የነበረው ተንሴ ማሞ
ለውጊያ ታጥቋል” የሚሉት የወንድሟ ቃላት ጆሮዋ ላይ አቃጨሉ::እሷንና ኢያሱን መግደል መፈለጉ አስገረማት። ኢያሱን መግደል የሚለው ቃል ዘገነናት። ልጄን በደንብ ማስጠበቅ አለብኝ አለች።
አምላኬ ልዤን ዐደራህን አለች፣ ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ
መስኮቱ እየሄደች። በስተቀኝ በኩል በባሏ ግንብና በፈረስ ቤቱ መሃል ያለው ሰፊ ቦታ ላይ ኢያሱ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ባልደራሱ ያነጋግረዋል።ወደ ግቢው በር እየጠቆመ ሌባ ጣቱን ያወዛውዛል። አትውጣ ተብለሀል
ነው ሚለው አለች፣ ምንትዋብ።
በፈረሱ ዙርያ በርካታ የመሣፍንት ልጆች እየተሯሯጡ ይጫወታሉ።
አሁን እስቲ እኼ ትንሽ ልዥ ምን አረገው? ለአልጋ ብሎ ትንሽ ልዥ
ይገድላል? እሱ እንደሆን አይቀመጥበት። ደሞ ማነም ሆነ ማን ኸወህኒ አምባ ቢመጣ የኢያሱን አልጋ አይወስድም. ቁሜ ነው ሙቼ።ልዤንም አልጋውንም እከላከላለሁ አለች። ኢያሱን እያየች፣ እንደነዝኸ ልዥች በመጫወቻው ሰዐት ለሞት ሊዳርግብኝ ባሏ ያስገነቡትን
ግንብ አየችና አስታወሰቻቸው። ለካንስ እንደዝኸ እያመጡ ነው ሰላም ሲነሷቸው የከረሙት.
ኧረ ደሞ ተንሴ ማሞ ተሹሞ ኸነበረ ላይሻር ኑሯል? ስንቱ ይሻር
የለ? ሹም ሽረት ያለ ነው። ደሞ ሰነባበተ እኮ። እንዴት ያለ በቀለኛ
እያሰበችበት ስትመጣ የጋለ ስሜት በመላ አካላቷ ተሰራጨ። ጉንጫፍም መሰለ።
እኔ ምንትዋብ ምን መስየዋለሁ? ቁጭ ብየ ምጠብቀው ይመስለዋል? ይኼ ኸመጣማ አልመለስለትም፡፡ እስቲ ልዤን እንድች ብሎ ንክች ያርግ ያየኛል፣ ብላ ቀኝ እጇን ጨብጣ የመስኮቱን ደፍ መታ መታ አደረገችው። እስቲ አሁን ሰላም ሆንን ስል... ስንት ነገር ላገሬ ሳስብ እንደዝኸ ያለው ይምጣ ላገሬ ያሰብሁትን ሳላረግማ እሱ አይቀድመኝም ኸመንገዴ ላይማ አይቆምም፤ እፋለመዋለሁ። ግድ የለም መልሸ ሰላም አመጣለሁ። አንዴ የሱን ነገር ልወጣ።
ተመልሳ ሄዳ ዙፋኗ ላይ ተቀመጠች። አሁን ብናደድ ምንም ጥቅም የለው። ይልቅስ ማረግ ያለብኝን ባስብ ነው ሚሻል። በመዠመሪያ የግቢውን በሮች እንዲዘጉ ማረግ አለብኝ መጠለያ እንዳይሆናቸው ደሞ ኸግቢ ውጭ ያሉትን ዛፎች ቅርንጫፍ ሁሉ ማስቆረጥ። አሁን
ይልቅ መሣፍንቱን፣ የጦር አበጋዞቹንና መኳንንቱን ተሎ ላነጋግር።ወልድየም ተሎ ብሎ ወሎና ጎዣም መልክት ይላክ፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...ከራስ ቢትወደድ ዘጊዮርጊስ መሸነፍ በኋላ፣ ሰላም ቀስ በቀስ በሃገሪቱ መልሶ ሰፈነ። ምንትዋብ በነገሠች በዓመቱ እንደ ቀድሞ ነገሥታት የራሷ የሆነ ቤተመንግሥት ለማሠራት ያደረባትን ጽኑ ፍቅርና ፍላጎት
ለማርካት ከባለቤቷ ከአፄ በካፋ ግንብ ጎን ቆማ ያሠራችው የተዋበውና የረቀቀው ፣ እንደ ሌሎቹ ግንቦች ሁሉ ባለ ሰቀሰቁና ባለ ሁለት ደርቡ ቤተመንግሥት የተደነቀ ሆነላት።
አፄ በካፋ በሞቱ በሁለተኛ ዓመታቸው ላይ ያሳደጓት፣ ያስተማሯት፣ በቤተመንግሥት ሥርዐት ሆነ በአስተዳደር ታንጻ እንድትወጣ የረዷት፣ አንደበተ ርቱዕዋ፣ የቤተክህነት ትምህርትና የቤተመንግሥት ወግ አዋቂዋ አያቷ ወይዘሮ ዮልያና ይህችን ምድር ጥለው ሄዱ። እሷ
ሆነች እናቷ መሪር ሐዘን ገባቸው። ዮልያና ታላቅ የቀብር ሥርዐት
ተደርጎላቸው ተቀባሩ። ምንትዋብ ተዝካራቸውንም ታላቅ ድግስ ደግሳ አወጣች።
ዮልያና በሞቱ በስድስተኛ ወራቸው ታናሽ ወንድማቸው ኒቆላዎስ ዐረፈ። ምንትዋብ ተጎዳች። ሆኖም ኒቆላዎስ በታላቅ ለቅሶና ሐዘን ተገቢው ሥርዐት ተደርጎለት ተቀበረ። ቀድሞውንም ቢሆን ለአፄ በካፋ ሁነኛ የነበረና በኋላም፣ ከእሷ ቀጥሎ ትልቁ ባለሥልጣን የነበረ፣አጋሯና በማንኛውም መንገድ ሲያግዛት፣ ሲያማክራትና ትዕዛዞቿን ሁሉ በተገቢው መንገድ ሲያስፈጽምላትና ሲፈጽምላት የቆየ ቀኝ እጇ በመሆኑ፣ የእሱ መሞት በቤተመንግሥት ውስጥ ትልቅ ክፍተት ፈጠረ።
ኒቆላዎስ ከሞተ ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ ምንትዋብና ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ዐዲሱ ቤተመንግሥት እልፍኝ ውስጥ እጅ የሚነሱትን መሣፍንትና መኳንንት አሰናብተው ጨርሰው፣ ኢያሱ ከአጃቢዎቹ ጋር ወጥቷል።
ምንትዋብም እልፍኟ ለመግባት ዝግጅት ላይ ነች፡፡ ደጃዝማች
ወልደልዑል ጫማውን ሳያወልቅ እልፍኝ ዘው ሲል ከአረማመዱ የሆነ ነገር እንደገጠመው አወቀች። ዛሬ ወልድየ ምንን ሁኖ ነው አለወትሮው በችኮላ ሚራመደው አለች፣ ትኩር ብላ እያየችው።
“ችግር አለ” አላት፣ የችኮላ ሰላምታ ከሰጣት በኋላ።
“የምን ችግር ወልድየ?” ከተቀመጠችበት ተነሳች።
“የጃንሆይ መኰንን የነበረው ተንሴ ማሞ ለውጊያ ታጥቋል።”
“ምን ይሁን ብሎ?” ፊቷ ጥላ ጣለበት። “ምን ይሁን ብሎ ነው አሁን ጦር ይዞ ሚነሳ?”
“ኸኢያሱ ክፍል የለኝም ብሎ። ያው ፊት እንደሰማነው፣ እኒህ
ቋረኞች እስተመቸ ነው ሚገዙን ብሎ።”
ከቋራ ስለመምጣቷ ከአያቷ ጋር ሲያወሩ፣ “ንቀታቸው... ወደ ፊት
ታቂዋለሽ” ያሉት ትዝ አላትና ራሷን በትዝብት ነቀነቀች። “እኒህ
ቋረኞች እስተመቸ ነው ሚገዙን ብሎ?” አለችና ከት ብላ የምጸት ሳቅ ሳቀች።
“አዎ እስተመቸ ነው ሚገዙን እያለ ሲቆጭ ቆይቷል” አላትና
እንድትቀመጥ በእጁ ዙፋኗን አመለከታት።
ቀጥል በሚል እጇን አወዛወዘችለት።
“አንዱም ኸተሰጠው የዳሞት ገዥነት ስለወረደ በልቡ ቂም ኣሳድሮ ነው እኼን ሊያረግ የተነሳው። ጥላቻውና እብሪቱ መጠን አጥቶ እዋጋለሁ ብሎ ነገሩን ኻዘጋጀ ሰንብቷል። “
እኼን የኩበት ካብ ሳላፈርስ
ሰው አልባልም ብሏል አሉ።”
“የኩበት ካብ?”
“የንጉሥ ኢያሱንና ያንቺን መንግሥት ማለቱ ነዋ!”
“ዛዲያማ ይጠብቀና” አለች፣ ሌባ ጣቷን እያወዛወዘች።
“ኸመጣሽ ዠምሮ ቋረኞች ላይ ያለው ግምት ምን እንደሁ
ታውቂያለሽ። አንቺም ብትሆኚ አልተሸነፍሽላቸውም፤ ወደፊትም
ታሸንፊያቸዋለሽ። ስሰማ ተንሴ ማሞ ኸዝኸ ሁሉ መጥቶ ግቢውን
አይቶ ነው አሉ የኸደው። ተመልሸ መጣለሁ ብሎ ዝቷል።”
“እንዴት ልቡ አብጧል በል? ይምጣ... ይምጣ... እስቲ እናያለን
የኩበት ካቡን ሲያፈርስ። የልዢን አልጋ ኻላስከበርሁማ እኔ ምንትዋብ ሰው ማዶለሁ” አለች።
ሰውነቷ ጋለ።
“አሳቡ አንቺንና ንጉሥ ኢያሱን መግደል ነው። መንገስ ሚፈልገውን ጠይቆ ሊመጣ ወህኒ ኸዷል። ወንድሙ ተስፋ ማሞም
ኸሱ ጋር አምጿል። ኸጎዣምም ብዙ ሠራዊት ሰብስቧል አሉ። እኛም መዘጋጀት አለብን።”
ለጥቂት ጊዜ ዝም ብላ አየችውና፣ “ሚነግሠውን ያምጣ። የትኛው
አልጋ ላይ እንደሚያስቀምጠው እናያለን። ይልቅስ አሁን ኸመሣፍንቱ፣ ኸመኳንንቱና ኸጦር አበጋዞቹ ጋር እንምከር። ለወሎና ለጎዣም ባላባትም ስለሁኔታው እናመላክታቸው። ዛሬውኑ መልክተኛ እንላክ።ጠንካራ ጦር ስላላቸው ኸነሱ ጋር ተባብረን ነው እኒህን ሰዎች መቋቋም
ምንችለው። ዛሬውኑ ሁነኛ ሰው ላክና እንዲደርሱልን አርግ::”
“በጀ፤ እንደሱ አረጋለሁ” ብሏት እጅ ነስቶ ወጣ።
የእልፍኝ አስከልካዩን ቴዎድሮስን አስጠራች።መኳንንቱና የጦር አበጋዞቹ በአስቸኳይ መሠሪ
እንዲነግራቸው ነገረችው። ኢያሱም ከግቢ እንዳይወጣ ትዕዛዝ ሰጠች።ቴዎድሮስ እጅ ነስቶ በፍጥነት ወጣ።
ዙፋኗ ላይ ተቀመጠች። “የጃንሆይ መኰንን የነበረው ተንሴ ማሞ
ለውጊያ ታጥቋል” የሚሉት የወንድሟ ቃላት ጆሮዋ ላይ አቃጨሉ::እሷንና ኢያሱን መግደል መፈለጉ አስገረማት። ኢያሱን መግደል የሚለው ቃል ዘገነናት። ልጄን በደንብ ማስጠበቅ አለብኝ አለች።
አምላኬ ልዤን ዐደራህን አለች፣ ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ
መስኮቱ እየሄደች። በስተቀኝ በኩል በባሏ ግንብና በፈረስ ቤቱ መሃል ያለው ሰፊ ቦታ ላይ ኢያሱ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ባልደራሱ ያነጋግረዋል።ወደ ግቢው በር እየጠቆመ ሌባ ጣቱን ያወዛውዛል። አትውጣ ተብለሀል
ነው ሚለው አለች፣ ምንትዋብ።
በፈረሱ ዙርያ በርካታ የመሣፍንት ልጆች እየተሯሯጡ ይጫወታሉ።
አሁን እስቲ እኼ ትንሽ ልዥ ምን አረገው? ለአልጋ ብሎ ትንሽ ልዥ
ይገድላል? እሱ እንደሆን አይቀመጥበት። ደሞ ማነም ሆነ ማን ኸወህኒ አምባ ቢመጣ የኢያሱን አልጋ አይወስድም. ቁሜ ነው ሙቼ።ልዤንም አልጋውንም እከላከላለሁ አለች። ኢያሱን እያየች፣ እንደነዝኸ ልዥች በመጫወቻው ሰዐት ለሞት ሊዳርግብኝ ባሏ ያስገነቡትን
ግንብ አየችና አስታወሰቻቸው። ለካንስ እንደዝኸ እያመጡ ነው ሰላም ሲነሷቸው የከረሙት.
ኧረ ደሞ ተንሴ ማሞ ተሹሞ ኸነበረ ላይሻር ኑሯል? ስንቱ ይሻር
የለ? ሹም ሽረት ያለ ነው። ደሞ ሰነባበተ እኮ። እንዴት ያለ በቀለኛ
እያሰበችበት ስትመጣ የጋለ ስሜት በመላ አካላቷ ተሰራጨ። ጉንጫፍም መሰለ።
እኔ ምንትዋብ ምን መስየዋለሁ? ቁጭ ብየ ምጠብቀው ይመስለዋል? ይኼ ኸመጣማ አልመለስለትም፡፡ እስቲ ልዤን እንድች ብሎ ንክች ያርግ ያየኛል፣ ብላ ቀኝ እጇን ጨብጣ የመስኮቱን ደፍ መታ መታ አደረገችው። እስቲ አሁን ሰላም ሆንን ስል... ስንት ነገር ላገሬ ሳስብ እንደዝኸ ያለው ይምጣ ላገሬ ያሰብሁትን ሳላረግማ እሱ አይቀድመኝም ኸመንገዴ ላይማ አይቆምም፤ እፋለመዋለሁ። ግድ የለም መልሸ ሰላም አመጣለሁ። አንዴ የሱን ነገር ልወጣ።
ተመልሳ ሄዳ ዙፋኗ ላይ ተቀመጠች። አሁን ብናደድ ምንም ጥቅም የለው። ይልቅስ ማረግ ያለብኝን ባስብ ነው ሚሻል። በመዠመሪያ የግቢውን በሮች እንዲዘጉ ማረግ አለብኝ መጠለያ እንዳይሆናቸው ደሞ ኸግቢ ውጭ ያሉትን ዛፎች ቅርንጫፍ ሁሉ ማስቆረጥ። አሁን
ይልቅ መሣፍንቱን፣ የጦር አበጋዞቹንና መኳንንቱን ተሎ ላነጋግር።ወልድየም ተሎ ብሎ ወሎና ጎዣም መልክት ይላክ፡
👍12
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ከስብሰባው እንደወጣች የክተት አዋጅ ጃን ተከል ላይ በሊጋባው አማካኝነት አስነገረች። ጐንደር አካባቢ ያለው ሠራዊት በአጣዳፊ እንዲሰለፍ አደረገች። ከሰዐት በኋላ፣ ጐንደር ያለ ሠራዊት ተሰበሰበ። ኩርዓት ሥርዐቱ መጥቶ ሠራዊቱ ለዘውዱ ሲል መሐላ እንዲገባ ጠየቀች። ሠራዊቱም፣ “አብረን ባንቆም፣ አብረን ባንታገል፣ እዝጊሃር
ይደምስሰን፤ ኸቴጌይቱና ኸንጉሡ በረከት አያሳትፈን” እያለ ማለ።
ምንትዋብ፣ ምግብ በተፋጠነ ሁኔታ ከቤተመንግሥት ቀህ በር
ለተሰበሰበው ሠራዊት እንዲታደል አደረገች። በቤተመንግሥቱ ዙርያ
ያሉት የዋርካ ቅርንጫፎች ተቆረጡ። የገባም እንዳይወጣ የወጣም እንዳይገባ አስራ ሁለቱም የቤተመንግሥት በሮች ተዘጉ።
በሁሉም በሮች መኳንንት ሠራዊት ይዘው እንዲቆሙ አስደረገች።
በተለይም ደግሞ ለጠላት መግቢያ ይሆናሉ ብላ በገመተቻቸው በሮች ላይ ጀግና የምትላቸውን መኳንንትና የጦር አበጋዞች አሰለፈች። የጦር
አበጋዞቹም ከቋራ፣ ከወገራ፣ ከከምከምና ከቃሮዳ በየቀኑ የሚገባውን ሠራዊት በሁሉም በሮች እንዲያስቆሙ አደረገች።
ልጇን ይዛ ከባለሟሎች ጋር በተዘክሮ በር ስትቆም፣ ታቦታትም
ከእነሱ ጎን ቆሙ። በጀግንነታቸውና በብልህነታቸው የተመሰገኑት ጦረኞች የዮልያና ልጅ ደጃዝማች አርከሌድስ፣ ብላቴን ጌታ ኤፍሬም፣
ፊታውራሪ ጎለም የመሳሰሉት ከጎኗ ተሰለፉ። ደጃዝማች ወልደልዑል ለውጊያ እንዲመቹ በየበሮቹ ላይ መስኮት መውጣት አለበት ብሎ በማሳሰቡ በሁሉም በሮች መስኮቶች ተከፈቱ።
የወህኒ ጠባቂው ቄርሎስ ከእነተንሴ ማሞ ጋር ተዋውሎና ለእነምንትዋብ የገባውን መሐላ ክዶ “ኢያሱ ሙቷል። መኳንንት ተመካክረው ሕዝቅያስ
ወረኛን አምጣ ተብያለሁ” ብሎ፣ ሕዝቅያስ ወረኛ የተባለውን የነጋሢ
ወገን ከወህኒ አውጥቶ፣ ለእነተንሴ ማሞ መስጠቱን ምንትዋብ ሰማች።ተንሴ ማሞ ሕዝቅያስን ይዞና በርካታ ጦር አስከትሎ በፍጥነት ጐንደር
መድረሱና ሠራዊቱ ቀሀ ወንዝ አጠገብ የጥምቀተ ባሕር ግቢ ውስጥ የመስፈሩ ዜና ደረሳት።
በቅርቡ ተሾመው የነበሩትና አፄ በካፋ በሞቱ ጊዜ ምንትዋብ
ለምክክር የጠራቻቸው እንደ እነቢትወደድ ላፍቶና ባሻ ኤልያስ
የመሳሰሉ መኳንንት ከተንሴ ማሞ ጋር ወገኑ። ምንትዋብ ስትሰማ
አዘነች። ወልደልዑል፣ “ሲሾሙና ሲሸለሙ፣ ጉልት ሲጎለቱ፣ ርስት
ሲተከሉ፣ ባረቄና በጠጅ ጉሮሯቸውን ሲያጥቡ የከረሙ ሁሉ ጊዜ አይተው መክዳታቸው አይቀርም” ያለውን አስታወሰች።
ትምህርት ተማረች።
የቀድሞው መኰንን ተንሴ ማሞ ጃን ተከል ወጥቶ፣ “ሕዝቅያስ
ነግሣል” ብሎ አሳወጀ። ሕዝቡ፣ መኳንንትና ወይዛዝርት ሳይቀሩ ከፍራቻ የተነሳ ለዐዲሱ ንጉሥ ለሕዝቅያስ እየወጡ ሰገዱ። ምንትዋብ ስትሰማ ወንድሟ ወልደልዑል፣ “ሰዉም ቢሆን ጦር ሲያነሱበት ኃይለኛው ጋር
ነው ሚወግን። ስለሚፈራ ለሱ ይነጠፋል” ያላት ትዝ አላትና ገረማት።
ካህናቱም ዐዲሱን ንጉሥ በማሕሌት ተቀበሉ።
ሠራዊቱንም ተከትለው እነምንትዋብ ባሉበት በተዘክሮ በር መጡ። ጦሩን አደራጅቶ
በተጠንቀቅ ይጠብቅ የነበረው ወልደልዑል የመጣውን ጦር በውጊያ አሸነፈ። በሌሎች በሮችም እንደዚሁ በተደረገው ውጊያ የምንትዋብ ጦር አሸነፈ።
እነተንሴ ማሞ ግን የበለጠ እየተጠናከሩ መጡ። በየበሩ እየተመለሱ ውጊያውን አፋፋሙት። በተዘክሮና በአደናግር በሮች በተለይ ውጊያ ተጧጧፈ። ደጃዝማች አርከሌድስ በሚዋጋበት በር ስለተሸነፈ፣ ዐማጽያን በሩን ሰብረው ገቡ። ያገኙትን መዘበሩ። ወርቅ ሰቀላን፣ አደናግርን፣ ርግብና ዙፋን ቤቶችን አቃጠሉ። አረቄና ጠላ እየጠጡ ተሳክረው በየቦታው ወድቀው ተሸነፉና፣ ከግቢ ተባረሩ።
ከውጭ ሴቶች ከማጀት ወጥተው እነተንሴ ማሞን ወግነው ለውጊያ
ታጠቁ። ወንዶቹንም በዜማና በፉከራ አነሳሱ። አዝማሪዎችም
አንተ ሰው
አንተ ሰው
ግንቡን ጣሰው፣ እያሉ የእነተንሴ ማሞን ሠራዊት አበረታቱ።
ለጊዜውም ቢሆን የጦርነቱ ዕጣና አቅጣጫ ወዴት እንደሚያዘነብል
ለማወቅ አስቸገረ።
የተንሴ ማሞ ሠራዊት እነምንትዋብን ለመግደል ተዘክሮ በርን ሰብሮ ሲገባ፣ የእነምንትዋብ ሠራዊት ሲሸበር ወልደልዑል ተበሳጨ። “የት ትሸሻለህ? ባለህበት ቁም” አላቸው፣ መሬቱን በሌባ ጣቱ እየጠቆመ።
ወደጎን፣ ወደፊት፣ ወደኋላ እየተንጎራደደ፣ እጁን እያወናጨፈ፣ “ቃል ለሰማይ ቃል ለምድር ይሁንብኝ። አንቺ ኸእግሬ ስር ኻልሸሸሽ እኔ አልሸሽም” አለ፣ መሬቱን እያየ። ፊት ለፊት፣ ጠመንጃ ለጠመንጃ፤
ሠይፍ ለሠይፍ፣ ጦር ለጦር፣ ጋሻ ለጋሻ ጠላቶቹን ገጠመ።
ተዘክሮ በር ድብልቅልቁ ወጣ። የስቃይ ጩኸት በቤተመንግሥት
ዙርያ አስተጋባ። ክፉኛ የቆሰለ ጓደኛውን፣ ወንድሙንና አጋሩን
ትከሻው ላይ አንጠልጥሎ ሊሸሽ ሲሞክር ከኋላው በጦር ሲወጋ ወይንም ሠይፍ ሲሻጥበት ከተሸከመው ጋር አብሮ ሲወድቅ፣ አካባቢው ደም ለበሰ፤ ሬሳ በሬሳ ሆነ፤ ቀውጢ ሆነ።
የሰው ልጅ ጭካኔ፣ በውስጡ ያለ ያልተገራ ፍጥረቱ ይፋ ወጣ ::
በጩቤ የተወጋው፣ በሠይፍ እጁ ወይ እግሩ የተጎመደው እጁን ወደ
ሰማይ ሰቅሎ “ድረሱልኝ!” “አድኑኝ!” “ልጅን ዐደራ! “ምሽቴን ዕደራ!”
“እናቴን ዐደራ” “ውሃ!” “አምላኬ ነፍሴን ተቀበላት!” ሲል ተማጸነ።
መሬት ላይ ወድቆ ነፍስያ የያዘውን ሁሉ ሞት እየዞረ ጎበኘ ::
በሁለቱም ወገን ብዙ ሰው አለቀ። ወልደልዑል፣ ተዘክሮን ሰብሮ
ለገባው የጠላት ጦር ክንዱን አሳየ፤ አሸነፈ። ነፍሱ የተረፈች የጠላት ጦር ፈረጠጠ። አፄ በካፋ የተከሉትን ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ግን አቃጠለ። ሌሎችን ቦታዎችንም እንዲሁ።
ጐንደር ይበልጡንም በማታ ጋየች፤ ቤቶች ተቃጠሉ። ንብረትና
ከብቶች ተዘረፉ፤ ሴቶች ተደፈሩ። እነተንሴ ማሞ ቀሀ ወንዝ አካባቢን
በመያዛቸው ውሃ ጠፋ። ጐንደር ለውሃ ጥምና ለሰቆቃ ተጋለጠች።
ሰዉ “ውሃ” እያለ ጮኸ። ሰዉም እንስሳውም እጁን ለሞት ሰጠ።
በቤተመንግሥቱ በሮች እንደገና ውጊያ አየለ። ብዙ ሰው አለቀ፤ ሬሳ
በየመንገዱ ወደቀ፤ የወደቀ ቁስለኛ የሚያነሳው አጣ። ከቤተመንግሥት ውጭ ያለውን የእህል ጉድጓድ የተንሴ ማሞ ጦር በመያዙ፣ ግቢው ውስጥ የምግብ እጥረት ተፈጠረ።
ጐንደር ፍዳዋን ኣየች።
እነተንሴ ማሞ አቡኑን፣ ዕጨጌውንና ካህናቱን ሰብስበው፣ “እቴጌንና ንጉሡን አውግዙልን፣ ኮተሊክ ቄሶች መጥተው ቤተመንግሥት ውስጥ
ኸንጉሡና ኸቴጌይቱ ጋር ተዘግቶባቸዋል” አሏቸው።
እነሱም፣ “ለቴጌይቱና ለንጉሡ እንጨት የሰበረ፣ ውሃ የቀዳ፣ የታዘዘ ሁሉ ቃለ ሐዋርያት ይሁንበት። ከንጉሡ ጎን ሁነህ ሕዝቅያስን የወጋህ ሁሉ ገዝተንሃል” ሲሉ ገዘቱ።
ሊቃውንቱ ግን ተቃወሙ። “እኼ ግዝት የሕገ ወጦች ግዝት ነው።
ወፈ ገዝት ነው” ብለው አወገዙ። ምንትዋብ ስትሰማ “የሆዳሞች ግዝት” አለችው።
የጃዊ አዛዥ ሆኖ ተሾሞ የነበረው ሻለቃ ወረኛና የሜጫው አዛዥ
ጊዮርጊስም ዘንድ “ተከበናል ፍጠኑ” ስትል መልዕክት ላከች። ተንሴ ማሞ ይህን ሲሰማ አፍዞ አደንግዞ ያስቀረው ዘንድ ሻለቃ ወረኛ ላይ አስማተኛ ላከበት። ወረኛ የመጣውን አስማተኛና ዐጃቢዎቹን በጦር አለችው።
ወግቶ ገደላቸው።
ተንሴ ማሞ ዓላማው እንዳልተሳካለት ሲሰማ ተበሳጭቶ ለወረኛ፣ እነምንትዋብ ሙተዋል። ሕዝቅያስ ነግዟል። በዚያው ባለህበት ሹመትህን አጥንተናል፤ አትምጣ። ኸጊዜው ሁን” ሲል ላከበት።
ሻለቃ ወረኛና አዛዥ ጊዮርጊስ ግን የጃዊና የሜጫን ቀስተኛ፣ ፈረሰኛ፣
ነፍጠኛ፣ እግረኛና ወንጭፈኛ ሠራዊት ይዘው ፈጥነው ጐንደር ገቡ።የተንሴ ማሞን ጦር ከበቡ። የእነምንትዋብ ጦር ሲያይል አቡኑ፣ “ስለ ንጉሡ ብላችሁ ብትሞቱ የሰማዕታት ክብር ታገኛላችሁ” ብለው ሰበኩ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ከስብሰባው እንደወጣች የክተት አዋጅ ጃን ተከል ላይ በሊጋባው አማካኝነት አስነገረች። ጐንደር አካባቢ ያለው ሠራዊት በአጣዳፊ እንዲሰለፍ አደረገች። ከሰዐት በኋላ፣ ጐንደር ያለ ሠራዊት ተሰበሰበ። ኩርዓት ሥርዐቱ መጥቶ ሠራዊቱ ለዘውዱ ሲል መሐላ እንዲገባ ጠየቀች። ሠራዊቱም፣ “አብረን ባንቆም፣ አብረን ባንታገል፣ እዝጊሃር
ይደምስሰን፤ ኸቴጌይቱና ኸንጉሡ በረከት አያሳትፈን” እያለ ማለ።
ምንትዋብ፣ ምግብ በተፋጠነ ሁኔታ ከቤተመንግሥት ቀህ በር
ለተሰበሰበው ሠራዊት እንዲታደል አደረገች። በቤተመንግሥቱ ዙርያ
ያሉት የዋርካ ቅርንጫፎች ተቆረጡ። የገባም እንዳይወጣ የወጣም እንዳይገባ አስራ ሁለቱም የቤተመንግሥት በሮች ተዘጉ።
በሁሉም በሮች መኳንንት ሠራዊት ይዘው እንዲቆሙ አስደረገች።
በተለይም ደግሞ ለጠላት መግቢያ ይሆናሉ ብላ በገመተቻቸው በሮች ላይ ጀግና የምትላቸውን መኳንንትና የጦር አበጋዞች አሰለፈች። የጦር
አበጋዞቹም ከቋራ፣ ከወገራ፣ ከከምከምና ከቃሮዳ በየቀኑ የሚገባውን ሠራዊት በሁሉም በሮች እንዲያስቆሙ አደረገች።
ልጇን ይዛ ከባለሟሎች ጋር በተዘክሮ በር ስትቆም፣ ታቦታትም
ከእነሱ ጎን ቆሙ። በጀግንነታቸውና በብልህነታቸው የተመሰገኑት ጦረኞች የዮልያና ልጅ ደጃዝማች አርከሌድስ፣ ብላቴን ጌታ ኤፍሬም፣
ፊታውራሪ ጎለም የመሳሰሉት ከጎኗ ተሰለፉ። ደጃዝማች ወልደልዑል ለውጊያ እንዲመቹ በየበሮቹ ላይ መስኮት መውጣት አለበት ብሎ በማሳሰቡ በሁሉም በሮች መስኮቶች ተከፈቱ።
የወህኒ ጠባቂው ቄርሎስ ከእነተንሴ ማሞ ጋር ተዋውሎና ለእነምንትዋብ የገባውን መሐላ ክዶ “ኢያሱ ሙቷል። መኳንንት ተመካክረው ሕዝቅያስ
ወረኛን አምጣ ተብያለሁ” ብሎ፣ ሕዝቅያስ ወረኛ የተባለውን የነጋሢ
ወገን ከወህኒ አውጥቶ፣ ለእነተንሴ ማሞ መስጠቱን ምንትዋብ ሰማች።ተንሴ ማሞ ሕዝቅያስን ይዞና በርካታ ጦር አስከትሎ በፍጥነት ጐንደር
መድረሱና ሠራዊቱ ቀሀ ወንዝ አጠገብ የጥምቀተ ባሕር ግቢ ውስጥ የመስፈሩ ዜና ደረሳት።
በቅርቡ ተሾመው የነበሩትና አፄ በካፋ በሞቱ ጊዜ ምንትዋብ
ለምክክር የጠራቻቸው እንደ እነቢትወደድ ላፍቶና ባሻ ኤልያስ
የመሳሰሉ መኳንንት ከተንሴ ማሞ ጋር ወገኑ። ምንትዋብ ስትሰማ
አዘነች። ወልደልዑል፣ “ሲሾሙና ሲሸለሙ፣ ጉልት ሲጎለቱ፣ ርስት
ሲተከሉ፣ ባረቄና በጠጅ ጉሮሯቸውን ሲያጥቡ የከረሙ ሁሉ ጊዜ አይተው መክዳታቸው አይቀርም” ያለውን አስታወሰች።
ትምህርት ተማረች።
የቀድሞው መኰንን ተንሴ ማሞ ጃን ተከል ወጥቶ፣ “ሕዝቅያስ
ነግሣል” ብሎ አሳወጀ። ሕዝቡ፣ መኳንንትና ወይዛዝርት ሳይቀሩ ከፍራቻ የተነሳ ለዐዲሱ ንጉሥ ለሕዝቅያስ እየወጡ ሰገዱ። ምንትዋብ ስትሰማ ወንድሟ ወልደልዑል፣ “ሰዉም ቢሆን ጦር ሲያነሱበት ኃይለኛው ጋር
ነው ሚወግን። ስለሚፈራ ለሱ ይነጠፋል” ያላት ትዝ አላትና ገረማት።
ካህናቱም ዐዲሱን ንጉሥ በማሕሌት ተቀበሉ።
ሠራዊቱንም ተከትለው እነምንትዋብ ባሉበት በተዘክሮ በር መጡ። ጦሩን አደራጅቶ
በተጠንቀቅ ይጠብቅ የነበረው ወልደልዑል የመጣውን ጦር በውጊያ አሸነፈ። በሌሎች በሮችም እንደዚሁ በተደረገው ውጊያ የምንትዋብ ጦር አሸነፈ።
እነተንሴ ማሞ ግን የበለጠ እየተጠናከሩ መጡ። በየበሩ እየተመለሱ ውጊያውን አፋፋሙት። በተዘክሮና በአደናግር በሮች በተለይ ውጊያ ተጧጧፈ። ደጃዝማች አርከሌድስ በሚዋጋበት በር ስለተሸነፈ፣ ዐማጽያን በሩን ሰብረው ገቡ። ያገኙትን መዘበሩ። ወርቅ ሰቀላን፣ አደናግርን፣ ርግብና ዙፋን ቤቶችን አቃጠሉ። አረቄና ጠላ እየጠጡ ተሳክረው በየቦታው ወድቀው ተሸነፉና፣ ከግቢ ተባረሩ።
ከውጭ ሴቶች ከማጀት ወጥተው እነተንሴ ማሞን ወግነው ለውጊያ
ታጠቁ። ወንዶቹንም በዜማና በፉከራ አነሳሱ። አዝማሪዎችም
አንተ ሰው
አንተ ሰው
ግንቡን ጣሰው፣ እያሉ የእነተንሴ ማሞን ሠራዊት አበረታቱ።
ለጊዜውም ቢሆን የጦርነቱ ዕጣና አቅጣጫ ወዴት እንደሚያዘነብል
ለማወቅ አስቸገረ።
የተንሴ ማሞ ሠራዊት እነምንትዋብን ለመግደል ተዘክሮ በርን ሰብሮ ሲገባ፣ የእነምንትዋብ ሠራዊት ሲሸበር ወልደልዑል ተበሳጨ። “የት ትሸሻለህ? ባለህበት ቁም” አላቸው፣ መሬቱን በሌባ ጣቱ እየጠቆመ።
ወደጎን፣ ወደፊት፣ ወደኋላ እየተንጎራደደ፣ እጁን እያወናጨፈ፣ “ቃል ለሰማይ ቃል ለምድር ይሁንብኝ። አንቺ ኸእግሬ ስር ኻልሸሸሽ እኔ አልሸሽም” አለ፣ መሬቱን እያየ። ፊት ለፊት፣ ጠመንጃ ለጠመንጃ፤
ሠይፍ ለሠይፍ፣ ጦር ለጦር፣ ጋሻ ለጋሻ ጠላቶቹን ገጠመ።
ተዘክሮ በር ድብልቅልቁ ወጣ። የስቃይ ጩኸት በቤተመንግሥት
ዙርያ አስተጋባ። ክፉኛ የቆሰለ ጓደኛውን፣ ወንድሙንና አጋሩን
ትከሻው ላይ አንጠልጥሎ ሊሸሽ ሲሞክር ከኋላው በጦር ሲወጋ ወይንም ሠይፍ ሲሻጥበት ከተሸከመው ጋር አብሮ ሲወድቅ፣ አካባቢው ደም ለበሰ፤ ሬሳ በሬሳ ሆነ፤ ቀውጢ ሆነ።
የሰው ልጅ ጭካኔ፣ በውስጡ ያለ ያልተገራ ፍጥረቱ ይፋ ወጣ ::
በጩቤ የተወጋው፣ በሠይፍ እጁ ወይ እግሩ የተጎመደው እጁን ወደ
ሰማይ ሰቅሎ “ድረሱልኝ!” “አድኑኝ!” “ልጅን ዐደራ! “ምሽቴን ዕደራ!”
“እናቴን ዐደራ” “ውሃ!” “አምላኬ ነፍሴን ተቀበላት!” ሲል ተማጸነ።
መሬት ላይ ወድቆ ነፍስያ የያዘውን ሁሉ ሞት እየዞረ ጎበኘ ::
በሁለቱም ወገን ብዙ ሰው አለቀ። ወልደልዑል፣ ተዘክሮን ሰብሮ
ለገባው የጠላት ጦር ክንዱን አሳየ፤ አሸነፈ። ነፍሱ የተረፈች የጠላት ጦር ፈረጠጠ። አፄ በካፋ የተከሉትን ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ግን አቃጠለ። ሌሎችን ቦታዎችንም እንዲሁ።
ጐንደር ይበልጡንም በማታ ጋየች፤ ቤቶች ተቃጠሉ። ንብረትና
ከብቶች ተዘረፉ፤ ሴቶች ተደፈሩ። እነተንሴ ማሞ ቀሀ ወንዝ አካባቢን
በመያዛቸው ውሃ ጠፋ። ጐንደር ለውሃ ጥምና ለሰቆቃ ተጋለጠች።
ሰዉ “ውሃ” እያለ ጮኸ። ሰዉም እንስሳውም እጁን ለሞት ሰጠ።
በቤተመንግሥቱ በሮች እንደገና ውጊያ አየለ። ብዙ ሰው አለቀ፤ ሬሳ
በየመንገዱ ወደቀ፤ የወደቀ ቁስለኛ የሚያነሳው አጣ። ከቤተመንግሥት ውጭ ያለውን የእህል ጉድጓድ የተንሴ ማሞ ጦር በመያዙ፣ ግቢው ውስጥ የምግብ እጥረት ተፈጠረ።
ጐንደር ፍዳዋን ኣየች።
እነተንሴ ማሞ አቡኑን፣ ዕጨጌውንና ካህናቱን ሰብስበው፣ “እቴጌንና ንጉሡን አውግዙልን፣ ኮተሊክ ቄሶች መጥተው ቤተመንግሥት ውስጥ
ኸንጉሡና ኸቴጌይቱ ጋር ተዘግቶባቸዋል” አሏቸው።
እነሱም፣ “ለቴጌይቱና ለንጉሡ እንጨት የሰበረ፣ ውሃ የቀዳ፣ የታዘዘ ሁሉ ቃለ ሐዋርያት ይሁንበት። ከንጉሡ ጎን ሁነህ ሕዝቅያስን የወጋህ ሁሉ ገዝተንሃል” ሲሉ ገዘቱ።
ሊቃውንቱ ግን ተቃወሙ። “እኼ ግዝት የሕገ ወጦች ግዝት ነው።
ወፈ ገዝት ነው” ብለው አወገዙ። ምንትዋብ ስትሰማ “የሆዳሞች ግዝት” አለችው።
የጃዊ አዛዥ ሆኖ ተሾሞ የነበረው ሻለቃ ወረኛና የሜጫው አዛዥ
ጊዮርጊስም ዘንድ “ተከበናል ፍጠኑ” ስትል መልዕክት ላከች። ተንሴ ማሞ ይህን ሲሰማ አፍዞ አደንግዞ ያስቀረው ዘንድ ሻለቃ ወረኛ ላይ አስማተኛ ላከበት። ወረኛ የመጣውን አስማተኛና ዐጃቢዎቹን በጦር አለችው።
ወግቶ ገደላቸው።
ተንሴ ማሞ ዓላማው እንዳልተሳካለት ሲሰማ ተበሳጭቶ ለወረኛ፣ እነምንትዋብ ሙተዋል። ሕዝቅያስ ነግዟል። በዚያው ባለህበት ሹመትህን አጥንተናል፤ አትምጣ። ኸጊዜው ሁን” ሲል ላከበት።
ሻለቃ ወረኛና አዛዥ ጊዮርጊስ ግን የጃዊና የሜጫን ቀስተኛ፣ ፈረሰኛ፣
ነፍጠኛ፣ እግረኛና ወንጭፈኛ ሠራዊት ይዘው ፈጥነው ጐንደር ገቡ።የተንሴ ማሞን ጦር ከበቡ። የእነምንትዋብ ጦር ሲያይል አቡኑ፣ “ስለ ንጉሡ ብላችሁ ብትሞቱ የሰማዕታት ክብር ታገኛላችሁ” ብለው ሰበኩ።
👍14🔥2
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ ከተንሴ ማሞ ጋር በተደረገው ውጊያ በእሱ ሆነ በእሷ በኩል ያለቀው ሰው ብዛት በአእምሮዋ እየተመላለሰ እያደር ሰላም ነሳት። ሰላም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ይበልጥ እንድትገነዘብ አደረጋት። ሰላምን በሃገሯ ውስጥ ለማረጋገጥ
የበለጠ ጠንክራ መስራትና የልጇን መንግሥት ማደላደል እንዳለባት
የበለጠ ተገነዘበች፤ የበለጠ ተጋች።
የልጇን መንግሥት ለማጠናከር ወልደልዑልን፣ ተንሴ ማሞን ባሸነፉ በዓመቱ ራስ ቢትወደድ ብላ ሾመችው። አፄ ፋሲለደስ ያሰሩት የራሶች መኖሪያ ራስ ግንብ ውስጥ እንዲገባ አደረገች።
ያሰበችውን ሁሉ ለማሳካት፣
ዘወትር ጠዋት አስራ ሁለት ሰዐት ላይ ዳዊቷን ደግማ የጸሎት መጽሐፏን አንብባ እንደጨረሰች ወይዛዝርት ልብሷን ያለብሷታል
ያስጌጧታል። ብሎም ቁርስ ታደርጋለች። አፈ ንጉሡ መጥቶ ፍትሕ ፈላጊ እንዳለ ካስታወቃት፣ ሦስት ሰዐት ላይ ዙፋን ችሎት ከኢያሱ ጋር ተሰይማ አቤቱታ ትሰማለች። ፍትሐ ነገሥት
ጠንቅቀው ከሚያውቁ መሃል የተመረጡት ዐራት አዛዦች ፍትሓ
ነገሥት እየጠቀሱ ፍርድ ሲያሰሙና ፍርዳቸውን ሲሰጡ ትሰማለች።መኳንንቱ አንድ በአንድ የሚሰጡትን የብይን ሐሳብ ታዳምጣለች።በመጨረሻም የተለየ የተለየ ፍርድ ካላት ትሰጣለች።
ሽንጎ እንደተነሳ እልፍኟ ትመለሳለች። ከልጇ ጋር ሆና መሣፍንት መኳንንትና ሌሎችም እጅ ይነሳሉ። እነሱን እንዳሰናበተች ዘወትር ለራሷ የምታቀርበው ጥያቄ እንዴት ላስተዳድር?” በመሆኑ ጉባኤ ጠርታ የልጇን መንግሥት ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላም ለማምጣትና ለሃገሯ
ያሰበችውን ለመሥራት፣ ያንገራገረ መኰንን ካለ ከጥል ይልቅ ዕርቅ
እየመረጠች ለዕርቅ ትደራደራለች።
ጥምረት መፍጠር ካለባት ጋር ጥምረት ትፈጥራለች፣ በጋብቻ
ማስተሳሰር ያለባትን ታስተሳስራለች፤ ማን ከማን ጋር መጋባት እንዳለበት ትወጥናለች። ብሎም የመሣፍንቱንና የመኳንንቱን ቀልብ መሳብ ብቻ ሳይሆን ድጋፋቸውንም አገኘች። ሊቃውንት አድናቂያቸው
ካህናት ደግሞ አክባሪያቸው በመሆኗ ሊፃረሯት ምክንያት አጡ።ደከመኝ፣ ታከተኝ ሳትል ያለ ዕረፍት ራሷን በሥራ ጠመደች።
ሙሉ ለሙሉ ለሃገሯ ሰላምና ደሕንነት ማሰቧ፣ ለልጇ ሕይወት መጨነቋ፣ ከተንሴ ማሞ ጋር የተደረገው ውጊያ ያሳደረባት ድካም፣ ተጽዕኖና ያለ ዕረፍት መሥራቷ፣ ስለ ራሷ የምታስብበት ጊዜ እንዳይኖራት አደረጋት።
በሏ ከሞቱ ሦስት ዓመታቸው ነው
አፍላ እድሜዋ ላይ
በመሞታቸው የልጅነት ጊዜዋ እንደዚሁ መጥፋቱ ክፉኛ አሳሰባት።ሕይወቷ ጨው ጎደለው፤ ድግስ ላይ እንደሚቀርበው አዋዜ፣ ድቁስና
የተሰነገ ቃርያ ማጣፈጫ አጣ። ቋራን ለቃ ቤተመንግሥት የገባች ቀን ሕይወት የፈነጠቀችላትን ብርሃን መልሳ እንደ ክረምት ሰማይ ግራጫ ያለበሰችባት መስሎ ተሰማት።
ሙሉ ፀጋዋንም ሰስታ የያዘችባት መሰላት።
ዳግማዊ ኢያሱ በትምህርቱ ጎበዝ፣ በቅኔ ትምህርቱም ብስል
አእምሮውን እያሳየ ቢመጣም፣ ከቤተመንግሥት ውጭ ወጥቶ መዘዋወርዐእና እንደማንኛውም ልጅ መጫወት በመፈለጉ ወደ ውጭ በወጣ ቁጥር
ምንትዋብ ነፍስና ስጋዋ ይላቀቃሉ። ጠባቂዎች ቢኖሩትም፣ ምንትዋብ
ክፉ ያሰበ ይገድልብኛል ብላ ስለምትሰጋ ከእሷው ጋር ካልሆነ ባይወጣ ትመርጣለች። የኢያሱ የተፋጠነ ዕድገት የደስታ ምንጭ ቢሆንላትም፣ ደጅ ደጁን ማለቱ ግን ተጨማሪ የጭንቀት መነሻ ሆኖባታል።
በዕረፍት ጊዜዋ ከተወሰኑ መኳንንትና የኣፄ በካፋ እህት
የወለተእስራኤል ልጅ ከሆነው ከኢያሱና ከካህናት ጋር ጨዋታ
ባትይዝ ኖሮ ሕይወት የበለጠ እየከበደችባት በመጣች። በተለይም ልዑል ኢያሱ ዘወትር ጠያቂዋ በመሆኑ የቅርብ ወዳጅ እየሆነ መጣ።
ዙርያዋን ከከበባትና ዘወትር ለሥልጣንና ለሹመት ከሚቁነጠነጠውና ከሚወዳደረው፣ ካባውን እያወናጨፈ ከሚከራከረው ባላባት ጎን እሱን ረጋ ብሎ ማየቷ አረጋጋት። ጨዋታው ደስ እያላት መጣ። ለስለስ ማለቱና ቁጥብነቱ ማረካት።
እቴጌ መሆን ታላቅ ነገር ነው። በአደባባይና በሸንጎ የምትታየው
ደርባባዋ፣ ጠንካራዋና ደስተኛዋ ምንትዋብ ግን መኝታ ቤቷ ስትገባ
ብቸኛ ነች። ልጇ ኢያሱ ስላደገ፣ ከእሱ ጋር አንድ መኝታ ቤት
መተኛቱን አቁመዋል ። መኝታ ቤቷ ስትገባ ክፍሉ ባዶ፣ አልጋዋ
ቀዝቃዛ ሆነው ይጠብቋታል። በተለይም ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐሳቡ፣ ጭንቀቱና መጠበቡ በርትቶባታል።
አንድ ማታ ነው። ሁለተኛ ደርብ ላይ ባለው መኝታ ቤቷ መስኮት
ውጭውን ትመለከታለች አንዳንዴ ከራሷ ጋር ለመሆን ስትፈልግ
እንደምታደርገው። መንፈሷ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ መረጋጋት አቅቶታል። ድፍን ጨለማው ላይ አፍጣ ቆየች። ለወራት ሲያስጨንቃት
የነበረው ሐሳብ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ ውስጥ ተንሸራቶ ገባ። እስተመቸ ብቻየን እቀመጣለሁ? የሚሉት ቃላት ከአፏ አፈትልከው ወጡ።ደነገጠች። የሰማት ሰው እንዳለም ለማወቅ በመስኮቱ ወደ ታች አየች።በአካባቢው ማንም ያለ አይመስልም።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስታወጣ ስታወርደው የነበረ ነገር ቢሆንም፣
እንደዚህ ከአፌ ይወጣል ብላ አልገመተችም። ነገሩን ዳግም ላታነሳ ከራሷ ጋር ቃል ተገባብታና አፍና የያዘችው ነገር ከአፏ አምልጠ ሲወጣ ተገረመች። መልሳ ስውር ወደ ሆነውና ምሥጢር ደብቆ ወደ እሚያስቀምጠው የሰውነቷ ክፍል ሰግስጋ ልታስገባው ሞከረች።
አዳምጭኝ እያለ የሚወተውተውን ድምፅ ግን ማስቆም አቃታት።
አወጣች፤ አወረደች። መፍትሔ እንደሌለው ተገነዘበችና በትካዜ ሄዳ አልጋዋ ላይ ጋደም አለች።
ጸሎት ልታደርስ ፈልጋ የጸሎት መጽሐፉን ከዕንጨት የተሠራውና
ከፊት ለፊቱ የመስቀል ቅርጽ ያለው ረጅሙ #አትሮኖሷ ላይ አጋድማ፣ ከአንዱ ጸሎት ወደ ሌላው ብታልፍ መንፈሷ አልረጋጋ አለ። ዛሬስ እዝጊሃር ይቅር ይበለኝ ጠሎቱም እምቢየው ብሎኛል። ገና ግዝየ ነው ዛዲያ ምን ልሥራ? ብላ ጋደም እንዳለች አካሏ በሥራ፣ ስሜቷ በሐሳብ ደክመው ነበርና እንቅልፍ ጣላት።
በጣሙን ያስደነቃትን ሕልም አየች።
እጅም፣ እግርም፣ ፊትም ሆነ ጭንቅላት የሌለው፣ ግን ባያሌው
ደስ የሚል፣ ብርሃን የተሞላው፣ ቀይ አበባ መሳይ ነገር የሚያናግራት ይመስላታል ።
“ምንትዋብ!”
“አቤት! አንተ ማነህ?”
“እኔ ፍቅር ነኝ። ፍቅር ታቂያለሽ?”
“አዎን፣ በልዥነቴ ጥላዬ ሚባል ልዥ ኋላም ባሌን አፈቅር ነበር።”
“ጥላዬ ኻይንሽ ስለራቀ ኸልብሽ ርቋል። ባልሽን ትወጂ ነበር።
ለፍቅር ገና ነበርሽ።”
“ፍቅር ምንድርነው?”
“እኔ አልገለጥም። ሕይወታችሁ ውስጥ ኻሉ ምሥጢሮች አንዱ ነኝ።እናንት ሰዎች እኔን ሙሉ ለሙሉ ማወቅ ስለተሳናችሁ እኔን ሊገልጹ ሚችሉ በቂ ቃላት አላደራጃችሁም። እኔን ትመኛላችሁ፣ ግና ነፍሳችሁ
ምትላችሁን አታዳምጡም። ጠቢቡ እንዳለው የመውደድ ቦታው ነፍስ ነው። ዛዲያ እኔን ለመሸከም ነፍሳችሁን ማዳመጥ ይጠይቃል።”
“እንዴ አሁን እኔ ኸልዤና ካገሬ የበለጠ ማፈቅረው አለ?”
“አየሸ ምንትዋብ እኔ አንድ ነኝ። እናንተ ግና የፍቅር ዓይነት
እያላችሁ አስር ቦታ ትከፋፍሉኛላችሁ። ፍቅር ማለት ሕይወት ማለት ነው፤ ሞትንም ስንኳ በፍቅር ማሸነፍ ይቻላል። ግና ፍቅር ለናንተ ሲያልቅ ያልቃል... ሲያረጅ ያረጃል። ኻንዱ ቀንሳችሁ ለሌላው ታበዛላችሁ። ለምሳሌ አሁን አንቺ ለልዥሽና ላገርሽ ያለሽ ፍቅር ልብሽን በሙሉ ስለገዛ ራስሽን ችላ ብለሻል። ስለዝኸ ሕይወት ሙሉ ትርጉሟን ልትለግስሽ አልቻላት አለ። ጭንቀት ሲፈታተንሽ ውሎ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ ከተንሴ ማሞ ጋር በተደረገው ውጊያ በእሱ ሆነ በእሷ በኩል ያለቀው ሰው ብዛት በአእምሮዋ እየተመላለሰ እያደር ሰላም ነሳት። ሰላም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ይበልጥ እንድትገነዘብ አደረጋት። ሰላምን በሃገሯ ውስጥ ለማረጋገጥ
የበለጠ ጠንክራ መስራትና የልጇን መንግሥት ማደላደል እንዳለባት
የበለጠ ተገነዘበች፤ የበለጠ ተጋች።
የልጇን መንግሥት ለማጠናከር ወልደልዑልን፣ ተንሴ ማሞን ባሸነፉ በዓመቱ ራስ ቢትወደድ ብላ ሾመችው። አፄ ፋሲለደስ ያሰሩት የራሶች መኖሪያ ራስ ግንብ ውስጥ እንዲገባ አደረገች።
ያሰበችውን ሁሉ ለማሳካት፣
ዘወትር ጠዋት አስራ ሁለት ሰዐት ላይ ዳዊቷን ደግማ የጸሎት መጽሐፏን አንብባ እንደጨረሰች ወይዛዝርት ልብሷን ያለብሷታል
ያስጌጧታል። ብሎም ቁርስ ታደርጋለች። አፈ ንጉሡ መጥቶ ፍትሕ ፈላጊ እንዳለ ካስታወቃት፣ ሦስት ሰዐት ላይ ዙፋን ችሎት ከኢያሱ ጋር ተሰይማ አቤቱታ ትሰማለች። ፍትሐ ነገሥት
ጠንቅቀው ከሚያውቁ መሃል የተመረጡት ዐራት አዛዦች ፍትሓ
ነገሥት እየጠቀሱ ፍርድ ሲያሰሙና ፍርዳቸውን ሲሰጡ ትሰማለች።መኳንንቱ አንድ በአንድ የሚሰጡትን የብይን ሐሳብ ታዳምጣለች።በመጨረሻም የተለየ የተለየ ፍርድ ካላት ትሰጣለች።
ሽንጎ እንደተነሳ እልፍኟ ትመለሳለች። ከልጇ ጋር ሆና መሣፍንት መኳንንትና ሌሎችም እጅ ይነሳሉ። እነሱን እንዳሰናበተች ዘወትር ለራሷ የምታቀርበው ጥያቄ እንዴት ላስተዳድር?” በመሆኑ ጉባኤ ጠርታ የልጇን መንግሥት ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላም ለማምጣትና ለሃገሯ
ያሰበችውን ለመሥራት፣ ያንገራገረ መኰንን ካለ ከጥል ይልቅ ዕርቅ
እየመረጠች ለዕርቅ ትደራደራለች።
ጥምረት መፍጠር ካለባት ጋር ጥምረት ትፈጥራለች፣ በጋብቻ
ማስተሳሰር ያለባትን ታስተሳስራለች፤ ማን ከማን ጋር መጋባት እንዳለበት ትወጥናለች። ብሎም የመሣፍንቱንና የመኳንንቱን ቀልብ መሳብ ብቻ ሳይሆን ድጋፋቸውንም አገኘች። ሊቃውንት አድናቂያቸው
ካህናት ደግሞ አክባሪያቸው በመሆኗ ሊፃረሯት ምክንያት አጡ።ደከመኝ፣ ታከተኝ ሳትል ያለ ዕረፍት ራሷን በሥራ ጠመደች።
ሙሉ ለሙሉ ለሃገሯ ሰላምና ደሕንነት ማሰቧ፣ ለልጇ ሕይወት መጨነቋ፣ ከተንሴ ማሞ ጋር የተደረገው ውጊያ ያሳደረባት ድካም፣ ተጽዕኖና ያለ ዕረፍት መሥራቷ፣ ስለ ራሷ የምታስብበት ጊዜ እንዳይኖራት አደረጋት።
በሏ ከሞቱ ሦስት ዓመታቸው ነው
አፍላ እድሜዋ ላይ
በመሞታቸው የልጅነት ጊዜዋ እንደዚሁ መጥፋቱ ክፉኛ አሳሰባት።ሕይወቷ ጨው ጎደለው፤ ድግስ ላይ እንደሚቀርበው አዋዜ፣ ድቁስና
የተሰነገ ቃርያ ማጣፈጫ አጣ። ቋራን ለቃ ቤተመንግሥት የገባች ቀን ሕይወት የፈነጠቀችላትን ብርሃን መልሳ እንደ ክረምት ሰማይ ግራጫ ያለበሰችባት መስሎ ተሰማት።
ሙሉ ፀጋዋንም ሰስታ የያዘችባት መሰላት።
ዳግማዊ ኢያሱ በትምህርቱ ጎበዝ፣ በቅኔ ትምህርቱም ብስል
አእምሮውን እያሳየ ቢመጣም፣ ከቤተመንግሥት ውጭ ወጥቶ መዘዋወርዐእና እንደማንኛውም ልጅ መጫወት በመፈለጉ ወደ ውጭ በወጣ ቁጥር
ምንትዋብ ነፍስና ስጋዋ ይላቀቃሉ። ጠባቂዎች ቢኖሩትም፣ ምንትዋብ
ክፉ ያሰበ ይገድልብኛል ብላ ስለምትሰጋ ከእሷው ጋር ካልሆነ ባይወጣ ትመርጣለች። የኢያሱ የተፋጠነ ዕድገት የደስታ ምንጭ ቢሆንላትም፣ ደጅ ደጁን ማለቱ ግን ተጨማሪ የጭንቀት መነሻ ሆኖባታል።
በዕረፍት ጊዜዋ ከተወሰኑ መኳንንትና የኣፄ በካፋ እህት
የወለተእስራኤል ልጅ ከሆነው ከኢያሱና ከካህናት ጋር ጨዋታ
ባትይዝ ኖሮ ሕይወት የበለጠ እየከበደችባት በመጣች። በተለይም ልዑል ኢያሱ ዘወትር ጠያቂዋ በመሆኑ የቅርብ ወዳጅ እየሆነ መጣ።
ዙርያዋን ከከበባትና ዘወትር ለሥልጣንና ለሹመት ከሚቁነጠነጠውና ከሚወዳደረው፣ ካባውን እያወናጨፈ ከሚከራከረው ባላባት ጎን እሱን ረጋ ብሎ ማየቷ አረጋጋት። ጨዋታው ደስ እያላት መጣ። ለስለስ ማለቱና ቁጥብነቱ ማረካት።
እቴጌ መሆን ታላቅ ነገር ነው። በአደባባይና በሸንጎ የምትታየው
ደርባባዋ፣ ጠንካራዋና ደስተኛዋ ምንትዋብ ግን መኝታ ቤቷ ስትገባ
ብቸኛ ነች። ልጇ ኢያሱ ስላደገ፣ ከእሱ ጋር አንድ መኝታ ቤት
መተኛቱን አቁመዋል ። መኝታ ቤቷ ስትገባ ክፍሉ ባዶ፣ አልጋዋ
ቀዝቃዛ ሆነው ይጠብቋታል። በተለይም ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐሳቡ፣ ጭንቀቱና መጠበቡ በርትቶባታል።
አንድ ማታ ነው። ሁለተኛ ደርብ ላይ ባለው መኝታ ቤቷ መስኮት
ውጭውን ትመለከታለች አንዳንዴ ከራሷ ጋር ለመሆን ስትፈልግ
እንደምታደርገው። መንፈሷ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ መረጋጋት አቅቶታል። ድፍን ጨለማው ላይ አፍጣ ቆየች። ለወራት ሲያስጨንቃት
የነበረው ሐሳብ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ ውስጥ ተንሸራቶ ገባ። እስተመቸ ብቻየን እቀመጣለሁ? የሚሉት ቃላት ከአፏ አፈትልከው ወጡ።ደነገጠች። የሰማት ሰው እንዳለም ለማወቅ በመስኮቱ ወደ ታች አየች።በአካባቢው ማንም ያለ አይመስልም።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስታወጣ ስታወርደው የነበረ ነገር ቢሆንም፣
እንደዚህ ከአፌ ይወጣል ብላ አልገመተችም። ነገሩን ዳግም ላታነሳ ከራሷ ጋር ቃል ተገባብታና አፍና የያዘችው ነገር ከአፏ አምልጠ ሲወጣ ተገረመች። መልሳ ስውር ወደ ሆነውና ምሥጢር ደብቆ ወደ እሚያስቀምጠው የሰውነቷ ክፍል ሰግስጋ ልታስገባው ሞከረች።
አዳምጭኝ እያለ የሚወተውተውን ድምፅ ግን ማስቆም አቃታት።
አወጣች፤ አወረደች። መፍትሔ እንደሌለው ተገነዘበችና በትካዜ ሄዳ አልጋዋ ላይ ጋደም አለች።
ጸሎት ልታደርስ ፈልጋ የጸሎት መጽሐፉን ከዕንጨት የተሠራውና
ከፊት ለፊቱ የመስቀል ቅርጽ ያለው ረጅሙ #አትሮኖሷ ላይ አጋድማ፣ ከአንዱ ጸሎት ወደ ሌላው ብታልፍ መንፈሷ አልረጋጋ አለ። ዛሬስ እዝጊሃር ይቅር ይበለኝ ጠሎቱም እምቢየው ብሎኛል። ገና ግዝየ ነው ዛዲያ ምን ልሥራ? ብላ ጋደም እንዳለች አካሏ በሥራ፣ ስሜቷ በሐሳብ ደክመው ነበርና እንቅልፍ ጣላት።
በጣሙን ያስደነቃትን ሕልም አየች።
እጅም፣ እግርም፣ ፊትም ሆነ ጭንቅላት የሌለው፣ ግን ባያሌው
ደስ የሚል፣ ብርሃን የተሞላው፣ ቀይ አበባ መሳይ ነገር የሚያናግራት ይመስላታል ።
“ምንትዋብ!”
“አቤት! አንተ ማነህ?”
“እኔ ፍቅር ነኝ። ፍቅር ታቂያለሽ?”
“አዎን፣ በልዥነቴ ጥላዬ ሚባል ልዥ ኋላም ባሌን አፈቅር ነበር።”
“ጥላዬ ኻይንሽ ስለራቀ ኸልብሽ ርቋል። ባልሽን ትወጂ ነበር።
ለፍቅር ገና ነበርሽ።”
“ፍቅር ምንድርነው?”
“እኔ አልገለጥም። ሕይወታችሁ ውስጥ ኻሉ ምሥጢሮች አንዱ ነኝ።እናንት ሰዎች እኔን ሙሉ ለሙሉ ማወቅ ስለተሳናችሁ እኔን ሊገልጹ ሚችሉ በቂ ቃላት አላደራጃችሁም። እኔን ትመኛላችሁ፣ ግና ነፍሳችሁ
ምትላችሁን አታዳምጡም። ጠቢቡ እንዳለው የመውደድ ቦታው ነፍስ ነው። ዛዲያ እኔን ለመሸከም ነፍሳችሁን ማዳመጥ ይጠይቃል።”
“እንዴ አሁን እኔ ኸልዤና ካገሬ የበለጠ ማፈቅረው አለ?”
“አየሸ ምንትዋብ እኔ አንድ ነኝ። እናንተ ግና የፍቅር ዓይነት
እያላችሁ አስር ቦታ ትከፋፍሉኛላችሁ። ፍቅር ማለት ሕይወት ማለት ነው፤ ሞትንም ስንኳ በፍቅር ማሸነፍ ይቻላል። ግና ፍቅር ለናንተ ሲያልቅ ያልቃል... ሲያረጅ ያረጃል። ኻንዱ ቀንሳችሁ ለሌላው ታበዛላችሁ። ለምሳሌ አሁን አንቺ ለልዥሽና ላገርሽ ያለሽ ፍቅር ልብሽን በሙሉ ስለገዛ ራስሽን ችላ ብለሻል። ስለዝኸ ሕይወት ሙሉ ትርጉሟን ልትለግስሽ አልቻላት አለ። ጭንቀት ሲፈታተንሽ ውሎ
👍7
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢያሱን ከሐሳቧ ማውጣት አቃታት። ጭንቅላቷ
ከእሱ ሌላ ማሰብ ተሳነው። ይኸ ሰው እኮ የጃንሆይ እት ልዥ ነው።
እንዴት ሁኖ ነው ኸሱ ጋር ሰውስ ምን ይላል? ይቅርብኝ ይኸ ነገር፡
አግባብ ማዶል። የጃንሆይ አጥንት ይወቅሰኛል። ለስሜም ለልዥም
ክብር ተገቢ ማዶል። ልዝም ቢሆን ሲያድግ ያባቴ ክብር ተነካ
ብሎ መቀየሙ አይቀርም፡፡ አምላኬ ምነው እንደዝኸ ያለ መፈታተኛ ሰጠኸኝ? እያለች አምላኳን ሞገተች።
የራሷን ፍላጎትና የሰዉን አመለካከት ስታወዳድር፣ ስታመዛዝን፣ስትጨነቅ፣ ልቧ ሲማስን ወራት አለፉ። ኢያሱ፣ መጥቶ እንደወትሯቸው
እንዳይጫወቱ ምክንያት እየሰጠች ከቤተመንግሥት እንዲርቅ አደረገችው። ውስጧ ለሚንቀለቀለውም ስሜት ልጓም ልታበጅለት ፈለገች። ኅሊናዋ አንዴ ሲከሳት፣ ሌላ ጊዜ ሲፈርድባት፣ አንቺ የቁስቋሟ፡
ይኸን ነገር ኸልቤ አውጭልኝ እያለች ማርያምን ተማፀነች።
ልቧ ግን ወደ እሱ አዘነበለ። የፍቅርን ዕርከን እያዘገመ ወጣ። እንደ እምቡጥ ጽጌሬዳ ራሱ የፈነዳና የአበበ ንፁህ ፍቅር በውስጡ ሰረፀ። በሠራ አካላቷ ተበተነ፣ ዐዲስ ሕይወት በመላ ሰውነቷ ውስጥ አንሰራራ፣
የጎደለው ልቧ ሞላ።
ኢያሱም ቢሆን አጎቱ ከሞቱ በኋላ፣ ቤተመንግሥት አዘውትሮ
መምጣቱ አለነገሩ እንዳልሆነ ገባት። የእሱም ልብ መዋለሉን ተረዳች።ከሰው መሀል ዝምታው ሲያነጋግራት፣ ዐይኖቿ የፍቅር ግብር ሲልኩ፣ገፅታው ጥያቄዎቿን ሲመልስላት ልቧ ከልቡ እንደተጣመረ አወቀች።
ኅሊናዋ መሞገቱን ተወ። ጭራሽ ገፋፋት፤ አሻፈረኝ፣ ባህልና ሥርዐት አያግደኝ በይ አላት።
የወደደ የተሸሽገን አያጣውም እንዲሉ፣ ኢያሱን ለብቻው እልፍኟ
ማስጠራት ጀመረች። ሲመጣ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ማውራትና
መጫወት ትፈልጋለች። ዘውዷን አውርዳ፣ ካባዋን ወርውራ፣ እቴጌ
ሳትሆን ሰው ሆና ትጠብቀዋለች።
መስተዋት ፊት ስትቆም፣ ዕድሜ አካሏ ላይ ያመጣውን ለውጥ
ለመፈተሽ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ ያቺ ቋራን ስትለቅ ዐዲስ የፈነዳ አበባ የመሰለችው ወጣት ዛሬ ዕድሜ ሰውነቷን ሞልቶ፣ አካሏንና አእምሮዋን አዳብሮ በውበት ላይ ውበት አክሎላት ገና የደረሰ ፍሬ መምሰሏ አልታወቅ ይላታል። ግንባሯን ፈታ፣ ጨምደድ አድርጋ፣ ወደ መስተዋቱ ጠጋ፣ ራቅ ስትል ያሉትም የሌሉትም መስመሮች ይታይዋታል። እህል በልቶ የሚያውቅ የማይመስለውን ወገቧን ወደ ጎን፣ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እያለች ትመለከትና ያች የቋራዋ ጉብል ኣልመስል ትላታለች፡፡
ያን ሰዐት ግዝየ ሌባ ነው ትላለች።
ኢያሱን ለብቻው ማግኘት ስትጀምር፣ ወሬው ከቤተመንግሥት ባለሟሎች ሹክሹክታ አልፎ መሣፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ካህናቱ፣ ሊቃውንቱና
ወይዛዝርቱ መሃል፣ ብሎም ሕዝቡጋ ደረሰ፤ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር ወዳጅነት ያዙ” እየተባለ ተናፈሰ።
ምንትዋብ ግን ወሬውን ከቁብም አልቆጠረችው።
ጭራሹን ከኢያሱ ጋር በድብቅ ተጋቡ። ጐንደሬዎች “ምልምል
የሚል ቅጽል ስም... የተመረጠው ለማለት... አወጡለት። ምንትዋብ
ምልምል እንዳይሉት ግራዝማች አለችው። ግራዝማች ኢያሱ የሰጣትን ዐዲስ የተገኘ ነፃነት ወደደችው። በልጅነቷ ቤተመንግሥት ገብታ ሕይወቷ በወግ ታጥሮ ቆይቶ አሁን እንደ ተራ ሰው መወደድ እናት መወደድ መቻሏ ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ሰጠው።
አንድ ቀን ግን ይህንን ትርጉም የሚገዳደር፣ ነፃነቷን የሚያውክ ነገር ተፈጠረ። ጠዋት ላይ እልፍኟ ተቀምጣ በሐሳብ ዥው ብላለች፤ ከፊሉን ጊዜ ስለ ኢያሱ፣ ከፊሉን ጊዜ ደግሞ ስለ ግብር አዳራሽ ግንባታ ታስባለች።
ዋና የእልፍኝ አስከልካዩ አርከኤድስ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና፣ “አንድ መነኩሴ ኸነማይ መልክት ይዤ መጥቻለሁ ብለው በር ላይ ናቸው።
የውጭ በር ላይ አላስገባ ብለዋቸው መመላለሳቸውን ብሰማ፣ ግቢ እንዲገቡ አርጌ አነጋገርኳቸው። 'ስመላለስ ከረምሁ፣ ብዙም ተጉላላሁ።
አገሬ መመለሻ ግዝየ በመጉላላት አለፈ። ለእቴጌ በእጅ ስጥ ተብየ
ይዤ የመጣሁትን መልክት እንዴት አድርጌ ይዤ መለሳለሁ እያልሁ
ኸዝሁ ከረምሁ እያሉ ቢጨነቁ ይጠብቁ ብያቸው መጣሁ” አላት።
“ኸነማይ?” አለች፣ ምንትዋብ ተገርማ። ከነማይ ማን መልዕክት
ሊልክላት እንዲሚችል መገመት አቅቷት።
“አዎ... ዘመድ ልኮኝ ነው አሉ። የተጠቀለለ ነገር ይዘዋል። “ለእቴጌ በጃቸው በቀር ለሌላ እንዳትሰጥ ብለው አስምለውኝ ነው ያመጣሁት ይላሉ።”
የማናቸው መነኩሴ? እያለች ትንሽ ካሰበች በኋላ፣ “ይግቡ!" አለችው።
አዛዥ አርከሌድስ እጅ ነስቶ ወጣ። ጥቂት ቆይቶ በእሱ መሪነት
ቆብ የደፉ፣ ረጅምና ሰፊ ቀሚስ ያጠለቁ፣ ሽማግሌ ሰው ገብተው
መሬት ሊስሙ ሲያጎነብሱ፣ “ግድ የለም አባቴ ይቀመጡ” አለቻቸው፣ ምንትዋብ።
ፈንጠር ብለው ወንበር ላይ ተቀመጡ።
“አባቴ ኸየት መጡ? ደሞስ ማን ልኮዎት ነው የመጡ?” አለቻቸው። መነኩሴው ከተቀመጡበት ተነሥተው ለጥ ብለው እጅ ነሱ። “እቴጌ ዝናዎን ስሰማ ቆይቸ ዛሬ እርሶን ለማየት ያበቃችኝ ኪዳነ ምረት
ምስጋና ይግባት። እቴጌ ኸነማይ ነው የመጣሁ። ደፈጫ ኪዳነ ምረት ስለት ነበረኝና እሱን ላደርስ መኸዴ ነው ብየ ስነሳ አንድ ኸኛ ዘንድ ሚመላለሱ ሰው፣ '
እኼን ለእቴጌ እንደምንም ብለው አድርሱልኝ። ዐደራ በእጅ ይስጡልኝ። ዘመድ ነኝ ቢሉኝ አመንኳቸው።”
“ሰውየው ማን ይባለሉ?”
“እቴጌ ዕቃውን ሲያዩ ማን እንደሆንሁ ያቃሉ ብለውኛል” ብለው ጥቅሉን አሳዩ።
ምንትዋብ፣ አርከሌድስን፣ “ተቀበልና ፍታው” አለችው።
“እቴጌ ኸርሶ በቀር ለሌላ አትስጥ ተብያለሁ” አሉ፣ መነኩሴው፣
ብድግ ብለው።
“ይቀመጡ... ይስጡትና እኔ ፈታዋለሁ።”
ጥቅሉን ለአርከሌድስ ሲሰጡት ተቀብላ ስትፈታው ዐራት ማዕዘን
እንጨት ላይ የተሣለ የራሷ ምስል ነው። ነጠላ ተከናንባ ወፍታ ጊዮርጊስ ደጀሰላም ላይ ነው። መብረቅ የመታት ያህል ክው ብላ ቀረች።
መነኩሴው የፊቷን መለዋወጥ አይተው ደነገጡ። ከተቀመጡበት
ተነሱ። “እቴጌ... ክፉ ነገር ኑሯል?” ሲሉ ጠየቋት።
የለ፣ ደግ ነው። ብቻ ያልጠበቅሁት ነገር ሁኖብኝ ነው። የላክሁ
ሰውየ ስማቸው ማነው ነበር ያሉኝ?”.
ስማቸውን ስንኳ አላወቅሁም። እኔ ብዙ ግዝየን ኸሰው ስለማልገናኝ
ስለሰዎች እምብዛም አላውቅም። 'እነማይ ለጉዳይ መጠቼ፣ ጐንደር“
ይኸዳሉ ሲሉ ብሰማ ተላኩኝ ብየ ነው። ለእቴጌም ዘመድ ነኝ። የእቴጌ አያቶች እኮ ትውልዳቸው ኸዝሁ ኸኛው ዘንድ ነው ቢሉኝ ምን ከፋኝ ብየ ይዤ መጣሁ።”
“ወደ እነማይ በቅርቡ ይመለሳሉ?”
“ለርሶ መልክቴን ካደረስሁ እንግዲህ ነገ እነሳለሁ።”
“እንግዲያማ ደሕና ግቡ። ለላኩዎም ሰው ባክዎን ወደ ጐንደር ብቅ ይበሉ። እንደርሶ ያለ ሠዓሊ ፈልጋለሁ ይበሉልኝ” አለቻቸው።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢያሱን ከሐሳቧ ማውጣት አቃታት። ጭንቅላቷ
ከእሱ ሌላ ማሰብ ተሳነው። ይኸ ሰው እኮ የጃንሆይ እት ልዥ ነው።
እንዴት ሁኖ ነው ኸሱ ጋር ሰውስ ምን ይላል? ይቅርብኝ ይኸ ነገር፡
አግባብ ማዶል። የጃንሆይ አጥንት ይወቅሰኛል። ለስሜም ለልዥም
ክብር ተገቢ ማዶል። ልዝም ቢሆን ሲያድግ ያባቴ ክብር ተነካ
ብሎ መቀየሙ አይቀርም፡፡ አምላኬ ምነው እንደዝኸ ያለ መፈታተኛ ሰጠኸኝ? እያለች አምላኳን ሞገተች።
የራሷን ፍላጎትና የሰዉን አመለካከት ስታወዳድር፣ ስታመዛዝን፣ስትጨነቅ፣ ልቧ ሲማስን ወራት አለፉ። ኢያሱ፣ መጥቶ እንደወትሯቸው
እንዳይጫወቱ ምክንያት እየሰጠች ከቤተመንግሥት እንዲርቅ አደረገችው። ውስጧ ለሚንቀለቀለውም ስሜት ልጓም ልታበጅለት ፈለገች። ኅሊናዋ አንዴ ሲከሳት፣ ሌላ ጊዜ ሲፈርድባት፣ አንቺ የቁስቋሟ፡
ይኸን ነገር ኸልቤ አውጭልኝ እያለች ማርያምን ተማፀነች።
ልቧ ግን ወደ እሱ አዘነበለ። የፍቅርን ዕርከን እያዘገመ ወጣ። እንደ እምቡጥ ጽጌሬዳ ራሱ የፈነዳና የአበበ ንፁህ ፍቅር በውስጡ ሰረፀ። በሠራ አካላቷ ተበተነ፣ ዐዲስ ሕይወት በመላ ሰውነቷ ውስጥ አንሰራራ፣
የጎደለው ልቧ ሞላ።
ኢያሱም ቢሆን አጎቱ ከሞቱ በኋላ፣ ቤተመንግሥት አዘውትሮ
መምጣቱ አለነገሩ እንዳልሆነ ገባት። የእሱም ልብ መዋለሉን ተረዳች።ከሰው መሀል ዝምታው ሲያነጋግራት፣ ዐይኖቿ የፍቅር ግብር ሲልኩ፣ገፅታው ጥያቄዎቿን ሲመልስላት ልቧ ከልቡ እንደተጣመረ አወቀች።
ኅሊናዋ መሞገቱን ተወ። ጭራሽ ገፋፋት፤ አሻፈረኝ፣ ባህልና ሥርዐት አያግደኝ በይ አላት።
የወደደ የተሸሽገን አያጣውም እንዲሉ፣ ኢያሱን ለብቻው እልፍኟ
ማስጠራት ጀመረች። ሲመጣ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ማውራትና
መጫወት ትፈልጋለች። ዘውዷን አውርዳ፣ ካባዋን ወርውራ፣ እቴጌ
ሳትሆን ሰው ሆና ትጠብቀዋለች።
መስተዋት ፊት ስትቆም፣ ዕድሜ አካሏ ላይ ያመጣውን ለውጥ
ለመፈተሽ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ ያቺ ቋራን ስትለቅ ዐዲስ የፈነዳ አበባ የመሰለችው ወጣት ዛሬ ዕድሜ ሰውነቷን ሞልቶ፣ አካሏንና አእምሮዋን አዳብሮ በውበት ላይ ውበት አክሎላት ገና የደረሰ ፍሬ መምሰሏ አልታወቅ ይላታል። ግንባሯን ፈታ፣ ጨምደድ አድርጋ፣ ወደ መስተዋቱ ጠጋ፣ ራቅ ስትል ያሉትም የሌሉትም መስመሮች ይታይዋታል። እህል በልቶ የሚያውቅ የማይመስለውን ወገቧን ወደ ጎን፣ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እያለች ትመለከትና ያች የቋራዋ ጉብል ኣልመስል ትላታለች፡፡
ያን ሰዐት ግዝየ ሌባ ነው ትላለች።
ኢያሱን ለብቻው ማግኘት ስትጀምር፣ ወሬው ከቤተመንግሥት ባለሟሎች ሹክሹክታ አልፎ መሣፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ካህናቱ፣ ሊቃውንቱና
ወይዛዝርቱ መሃል፣ ብሎም ሕዝቡጋ ደረሰ፤ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር ወዳጅነት ያዙ” እየተባለ ተናፈሰ።
ምንትዋብ ግን ወሬውን ከቁብም አልቆጠረችው።
ጭራሹን ከኢያሱ ጋር በድብቅ ተጋቡ። ጐንደሬዎች “ምልምል
የሚል ቅጽል ስም... የተመረጠው ለማለት... አወጡለት። ምንትዋብ
ምልምል እንዳይሉት ግራዝማች አለችው። ግራዝማች ኢያሱ የሰጣትን ዐዲስ የተገኘ ነፃነት ወደደችው። በልጅነቷ ቤተመንግሥት ገብታ ሕይወቷ በወግ ታጥሮ ቆይቶ አሁን እንደ ተራ ሰው መወደድ እናት መወደድ መቻሏ ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ሰጠው።
አንድ ቀን ግን ይህንን ትርጉም የሚገዳደር፣ ነፃነቷን የሚያውክ ነገር ተፈጠረ። ጠዋት ላይ እልፍኟ ተቀምጣ በሐሳብ ዥው ብላለች፤ ከፊሉን ጊዜ ስለ ኢያሱ፣ ከፊሉን ጊዜ ደግሞ ስለ ግብር አዳራሽ ግንባታ ታስባለች።
ዋና የእልፍኝ አስከልካዩ አርከኤድስ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና፣ “አንድ መነኩሴ ኸነማይ መልክት ይዤ መጥቻለሁ ብለው በር ላይ ናቸው።
የውጭ በር ላይ አላስገባ ብለዋቸው መመላለሳቸውን ብሰማ፣ ግቢ እንዲገቡ አርጌ አነጋገርኳቸው። 'ስመላለስ ከረምሁ፣ ብዙም ተጉላላሁ።
አገሬ መመለሻ ግዝየ በመጉላላት አለፈ። ለእቴጌ በእጅ ስጥ ተብየ
ይዤ የመጣሁትን መልክት እንዴት አድርጌ ይዤ መለሳለሁ እያልሁ
ኸዝሁ ከረምሁ እያሉ ቢጨነቁ ይጠብቁ ብያቸው መጣሁ” አላት።
“ኸነማይ?” አለች፣ ምንትዋብ ተገርማ። ከነማይ ማን መልዕክት
ሊልክላት እንዲሚችል መገመት አቅቷት።
“አዎ... ዘመድ ልኮኝ ነው አሉ። የተጠቀለለ ነገር ይዘዋል። “ለእቴጌ በጃቸው በቀር ለሌላ እንዳትሰጥ ብለው አስምለውኝ ነው ያመጣሁት ይላሉ።”
የማናቸው መነኩሴ? እያለች ትንሽ ካሰበች በኋላ፣ “ይግቡ!" አለችው።
አዛዥ አርከሌድስ እጅ ነስቶ ወጣ። ጥቂት ቆይቶ በእሱ መሪነት
ቆብ የደፉ፣ ረጅምና ሰፊ ቀሚስ ያጠለቁ፣ ሽማግሌ ሰው ገብተው
መሬት ሊስሙ ሲያጎነብሱ፣ “ግድ የለም አባቴ ይቀመጡ” አለቻቸው፣ ምንትዋብ።
ፈንጠር ብለው ወንበር ላይ ተቀመጡ።
“አባቴ ኸየት መጡ? ደሞስ ማን ልኮዎት ነው የመጡ?” አለቻቸው። መነኩሴው ከተቀመጡበት ተነሥተው ለጥ ብለው እጅ ነሱ። “እቴጌ ዝናዎን ስሰማ ቆይቸ ዛሬ እርሶን ለማየት ያበቃችኝ ኪዳነ ምረት
ምስጋና ይግባት። እቴጌ ኸነማይ ነው የመጣሁ። ደፈጫ ኪዳነ ምረት ስለት ነበረኝና እሱን ላደርስ መኸዴ ነው ብየ ስነሳ አንድ ኸኛ ዘንድ ሚመላለሱ ሰው፣ '
እኼን ለእቴጌ እንደምንም ብለው አድርሱልኝ። ዐደራ በእጅ ይስጡልኝ። ዘመድ ነኝ ቢሉኝ አመንኳቸው።”
“ሰውየው ማን ይባለሉ?”
“እቴጌ ዕቃውን ሲያዩ ማን እንደሆንሁ ያቃሉ ብለውኛል” ብለው ጥቅሉን አሳዩ።
ምንትዋብ፣ አርከሌድስን፣ “ተቀበልና ፍታው” አለችው።
“እቴጌ ኸርሶ በቀር ለሌላ አትስጥ ተብያለሁ” አሉ፣ መነኩሴው፣
ብድግ ብለው።
“ይቀመጡ... ይስጡትና እኔ ፈታዋለሁ።”
ጥቅሉን ለአርከሌድስ ሲሰጡት ተቀብላ ስትፈታው ዐራት ማዕዘን
እንጨት ላይ የተሣለ የራሷ ምስል ነው። ነጠላ ተከናንባ ወፍታ ጊዮርጊስ ደጀሰላም ላይ ነው። መብረቅ የመታት ያህል ክው ብላ ቀረች።
መነኩሴው የፊቷን መለዋወጥ አይተው ደነገጡ። ከተቀመጡበት
ተነሱ። “እቴጌ... ክፉ ነገር ኑሯል?” ሲሉ ጠየቋት።
የለ፣ ደግ ነው። ብቻ ያልጠበቅሁት ነገር ሁኖብኝ ነው። የላክሁ
ሰውየ ስማቸው ማነው ነበር ያሉኝ?”.
ስማቸውን ስንኳ አላወቅሁም። እኔ ብዙ ግዝየን ኸሰው ስለማልገናኝ
ስለሰዎች እምብዛም አላውቅም። 'እነማይ ለጉዳይ መጠቼ፣ ጐንደር“
ይኸዳሉ ሲሉ ብሰማ ተላኩኝ ብየ ነው። ለእቴጌም ዘመድ ነኝ። የእቴጌ አያቶች እኮ ትውልዳቸው ኸዝሁ ኸኛው ዘንድ ነው ቢሉኝ ምን ከፋኝ ብየ ይዤ መጣሁ።”
“ወደ እነማይ በቅርቡ ይመለሳሉ?”
“ለርሶ መልክቴን ካደረስሁ እንግዲህ ነገ እነሳለሁ።”
“እንግዲያማ ደሕና ግቡ። ለላኩዎም ሰው ባክዎን ወደ ጐንደር ብቅ ይበሉ። እንደርሶ ያለ ሠዓሊ ፈልጋለሁ ይበሉልኝ” አለቻቸው።
👍8
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።
ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።
አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።
ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።
ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።
“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”
“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-
ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።
ፈገግ አለ።
ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።
እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"
“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።
“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።
አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።
ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።
ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።
ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።
ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።
ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።
ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::
ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።
የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።
ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።
ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።
“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።
ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።
አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።
ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።
ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።
“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”
“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-
ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።
ፈገግ አለ።
ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።
እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"
“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።
“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።
አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።
ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።
ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።
ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።
ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።
ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።
ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::
ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።
የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።
ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።
ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።
“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
👍10
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ አልጣሽ የተባለችውን ሁለተኛ ልጇን ወልዳ ከአራስ ቤት እንደወጣች እንደገና በግዛት ዘመኗ ልትፈጽማቸው ያሰበቻቸው ነገሮች ላይ ትኩረት አደረገች።
ትምህርት ቁስቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ ለማስጀመር ከብርሃን ሰገድ ኢያሱ ጋር መከረች። ብዙ ጊዜ እንደሚያደርጉት አንድ ቀን እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል።
ትክ ብላ አየችው። ፈንጣጣ ፊቱ ላይ ምንም ምልክት ሳይተው
ማለፉ ገረማት። በቁስቋም ረድኤት መዳኒቱ ሠርቷል። ይኸን የመሰለ መልኩን ሊያበላሽብኝ እሷ የቁስቋሟ ማረችልኝ፡፡ አሁን ኢያሱን የመሰለ ልዥ አለ? የተባረኩ እያለች በሐሳብ ጭልጥ ብላ ሄደች።
ኢያሱ በሐሳብ እንደነጎደች ኣውቆ ከሄደችበት እስክትመለስ ዐይን
ዐይኗን እያየ ጠበቃት።
“አያትህ ታላቁ ኢያሱ ለትምርት ብዙ ዋጋ ሚሰጡ ሰው ነበሩ…
አለችው፣ ከሄደችበት ስትመለስ።
“አውቃለሁ። አንቺም ነገርሽ ሁላ እንደሳቸው ነው። ደሞስ የሳቸው
ስም መቸ ኻፍሽ ጠፍቶ ያውቃል?”
ከት ብላ ስትስቅ እሱም ሳቀ።
“ስለ ትምርት ላወራህ ፈልጌ ነው የሳቸውን ስም ያነሳሁ” አለችው፣
ፈገግ ብላ። “በሳቸው ዘመን የተማሮች ቁጥር ኸዝኸ ኸደብረሥላሤ ስንኳ ብዙ ነበር ይላሉ። ስንክሳርም በብዛት የተጣፈው በሳቸው ግዝየ
ነው። እንደ ክፍለ ዮሐንስ የመሰሉ ሊቃውንትም ኸጎዣም ያመጡ
እሳቸው ናቸው። ሊቁ አዛዥ ከናፍሮም ቢሆኑ በሳቸው ግዝየ ነው የነበሩ። ዛዲያ ልነግርህ የፈለግሁት ቁስቋም ውስጥ ትምርት ቤት ማቆም ብቻ ሳይሆን፣ ለተማሮቹና ላስተማሮቹ ድጋፍ ማረግ አለብን
ሚለውን ነው።”
“እኔም ስለሱ ነግርሻለሁ እያልሁ ነበር። ሌላ ደሞ ባለፈው መጻሕፍት ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ እንዲመለሱ ፈልጋለሁ ስትይ
ማልነበር?”
"ትርጉም.... አዎ ስል ነበር። ሁሉ ባግባቡ ነው። ባለፈው መላከ
ጠሐይ ሮብዓምን ትርጉም ላይ ቢበረታ ብያቸው ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ሚመልሱ ሰዎች አምጥተው ሥራ እንዲዠምሩ ተደርጓል።
ለእነመላከ ጠሐይ ሃይማኖትን ሚያስተምረውንና ላገር ሚጠቅመውን ሁሉ እንዲያስተረጉሙ ነግሬያቸው እነሱ ተመካክረው ወስነዋል።”
"የትርጉም ሥራ ለገዳማቱ ቢሰጥ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቸ።”
“ዛዲያ ምን አለ... ይሰጣል ። በጎ አሳብ ነው። ትዛዝ ሰጣለሁ። እኔ
መቸም ቢሞላልኝ አገር ሁሉ መጻፍ በመጻፍ እንዲሆንና ትምርት
እንዲስፋፋ ነው ምፈልግ። እኔ ራሴም ብሆን አንድ ቀን ስለ እመቤታችን ማርያም ታምር አስጥፋለሁ ብየ አስባለሁ። ደሞ እሑድ እሑድ ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ግብር እናግባላቸው። አንተም ለነሱ ትልቅ ክብር አለህ። ቅኔም ተምረሀል። ቅኔ እውቀቴ እንዳንተ ባይሆንም፣ሊቃውንቱ ቅኔ ሲቀኙ ስሰማ መንፈሴ ሁሉ ይታደሳል። በተለይማ
የአክስትህን ልዥ እመት ወለተብርሃንን ስሰማ እንዳው እንደሳቸው ቅኔ በቻልሁ እላለሁ፡፡ አንተማ ኸኔም የበለጠ ትወዳቸዋለህ።”
የአክስቱ ልጅ ነገር ሲነሳ ፈገግ አለ። “ውነትሽ ነው እመት ወለተብርሃን ታላቅ የቅኔ ሊቅ ናቸው። እሑድ እሑድ ግብር ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ማግባት ያልሽው ተገቢ ነው። በተነጋገርነው መሠረትም በአካባቢው ወይን እንዲተከል ቦታ ብታስጠኚ። ቃሮዳ አየሩ ለወይን ተስማሚ ነው ሲሉ ሰምቻለሁ። ቅርብም ነው።”
“ውነትህ ነው። ዛሬውኑ ሰው ይላካል።”
ሁለቱም ዝም አሉ።
“ግና ካህናቱና ሊቃውንቱ... ምናለ ልብሳቸውን ቢያጠዱ?” አላት።
ያልጠበቀችው በመሆኑ ከት ብላ ሳቀች። “ልብሳቸውን እንዲያጥቡ
ማረግ ይቻላል ። በጐንደር ዙርያና በየገዳማቱ እንዶድ ኣስተክለን
ልብሳቸውን እንዲያጥቡ እናረጋለና” አለችው፣ አሁንም እየሳቀች።
“ዋናዎቹ ካህናት ደሞ የወርቅ ጫማ እንዲያረጉ ፈልጋለሁ።”
“ወርቅ አሳብ ነው። ይታዘዝላቸዋል። የአክብሮትህ ምልክት ነው።
እንደገና ዝም ብለው ተቀመጡ። ኢያሱ ሐሳብ የገባው ይመስላል።
እሷም ዝም ብላ ታየዋለች።
ዐይን ዐይኗን እያየ፣ “አደን ብኸድ ትፈቅጅልኛለሽ?” እናቱን ፈሪና
አክባሪ ነው።
ዕጢዋ ዱብ አለ። አፏ ተያዘ። ሊመጣበት የሚችለው አደጋ
አሳሰባት። ጥያቄው ግን አንድ ቀን እንደሚመጣ ታውቃለች።
“ኣባትህ ስንኳ በኸዱ ቁጥር እጨነቅ ነበር። ኢያሱ እንድትኸድ
አልፈልግም፤ ጭንቀቱን አልችለውም።”
“ምን ችግር አለው?”
“ባትኸድ መርጣለሁ። ኢያሱ አልጋውን እኮ ባየነቁራኛ ሚጠባበቅአለ!”
“ሁሉስ እያደኑ ማዶል እንዴ የኖሩት?”
“ገና ልዥ እኮ ነህ ኢያሱ።”
ድምጽዋ ተርበተበተ።
“አትጨነቂ። ምንም ሚመጣ ነገር የለም። ሰዎች ይዠ ነው ምኸደው
በዝኸ ላይ ደሞ አልቆይም።”
“ኻንተ መለየት አልፈቅድም ኢያሱ ... መቸ ትነሳለህ?”
ነገ።”
“ነገ?”
“አዎ! ነገ።”
“ታሰብህበት ቆይተሀል ማለት ነዋ! መቸስ ምን ኣረጋለሁ። ቁስቋም
ደሕና ትመልስህ። በጠሎቴ አልለይህም።”
አይዞሽ አትጨነቂ። በጠዋት ስለምኸድ ካሁኑ ልሰናበትሽ” አላት፣ጠዋት መጥቶ ቢሰናበታት እንባዋን ማየት ስለማይችል። ተነስታ ወደ እልፍኟ ስትሄድ በጭንቀት ተመለከታት።
በማግስቱ ጠዋት ከእናቷ ጋር በመስኮት ቆመው የአደን ዕቃው
በቅሎ ላይ ሲጫን አይተው ሆዳቸው ባባ። ኢያሱ ፈረሱ ቀርቦለት፡ በሹሩባው ዙርያ ነጭ ሻሽ አስሮ፣ ካባውን ደርቦ ከዐጀቡ ጋር ብቅ ሲል፣ የቤተመንግሥት ባለሟሉ፣ ወታደሩ፣ ጋሻ ጃግሬውና ሌላው ሰገደ።ምንትዋብና እናቷ ግን ሲቃ ያዛቸው።
ከቤተመንግሥት ግቢ ሲወጣ፣
ምንትዋብ ጩሂ ጩሂ አላት። እንኰዬ ትከሻዋን መታ መታ አደረጓት።እሳቸውም እንባ እንባ ብሏቸዋል፤ ግን እሷን ማረጋጋት መረጡ።
ሁለቱም በየክፍላቸው ገብተው ወገባቸውን በገመድ አስረው ሱባዔ ገቡ። መሬት ላይ ተኙ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ጸሎታቸው ሠምሮ ኢያሱ በሰላም ተመለሰ። እናትና ልጅ ገመድ ትጥቃቸውን ፈቱ።የነበሩበትን ጭንቀት ሳይናገሩ በደስታ ተቀበሉት።
እያደር የአደን ፍቅር በረታበት፤ መዝናኛው አደረገው። በሄደ ቁጥር
እናቱና አያቱ ወገባቸውን በገመድ ጠፍረው መሬት መተኛትና ሱባዔ
መግባት፣ ሲመጣ ደግሞ ገመዳቸውን ፈትተው መጣል፣ ጸማቸውን መፍታት ልማድ አደረጉት። እንደዚህ እያለም ኢያሱ የከፋ ነገር ሳይገጥመው ቀለል ያለ አደን ማካሄዱን ቀጠለ።
ከእናቱ ጋር በተስማሙት መሠረት ከንባብ ቤት እስከ ትርጓሜ ቤት
ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያምን በትምህርት ለማደራጀት ወጡ ወረዱ።ሁለት መቶ የሚጠጉ ምርጥ ሊቃውንት ከጐንደር ገዳማትና ከሌላ የሃገሪቱ ክፍሎች እየመጡ ወንበር ዘረጉ
የተማሪ ጎጆዎች ተቀለሱ። ትምህርት ከቁስቋም ሌላ በየገዳማቱና በየደብሮቹ ተስፋፋ። ወሬውን የሰማ ተማሪ ከየቦታው ፈልሶ ጐንደር ገባ፡፡ ጐንደር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ የሊቃውንት ማፍሪያና
መሰብሰቢያ ሆነች። ከጐንደር ውጭም ትምህርት ቤቶች ተስፋፉ።
የዜማ ሊቃውንት ድርጎ በማግኘታቸው ሙያቸውን አበለፀጉ ቤተክርስቲያንን አገለገሉ፤ ቤተመንግሥትንም አዝናኑ።
የሥዕል ሥራ በአያሌው አደገ። ቀለም አጠቃቀም ጥንት ከነበረው
ለውጥ አመጣ፣ የአቀራረብና የይዘት ለውጦች መጡ። ሠዓሊዎች ድጎማ እየተደረገላቸው አብያተ ክርስቲያናትን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አስጌጡ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ አልጣሽ የተባለችውን ሁለተኛ ልጇን ወልዳ ከአራስ ቤት እንደወጣች እንደገና በግዛት ዘመኗ ልትፈጽማቸው ያሰበቻቸው ነገሮች ላይ ትኩረት አደረገች።
ትምህርት ቁስቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ ለማስጀመር ከብርሃን ሰገድ ኢያሱ ጋር መከረች። ብዙ ጊዜ እንደሚያደርጉት አንድ ቀን እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል።
ትክ ብላ አየችው። ፈንጣጣ ፊቱ ላይ ምንም ምልክት ሳይተው
ማለፉ ገረማት። በቁስቋም ረድኤት መዳኒቱ ሠርቷል። ይኸን የመሰለ መልኩን ሊያበላሽብኝ እሷ የቁስቋሟ ማረችልኝ፡፡ አሁን ኢያሱን የመሰለ ልዥ አለ? የተባረኩ እያለች በሐሳብ ጭልጥ ብላ ሄደች።
ኢያሱ በሐሳብ እንደነጎደች ኣውቆ ከሄደችበት እስክትመለስ ዐይን
ዐይኗን እያየ ጠበቃት።
“አያትህ ታላቁ ኢያሱ ለትምርት ብዙ ዋጋ ሚሰጡ ሰው ነበሩ…
አለችው፣ ከሄደችበት ስትመለስ።
“አውቃለሁ። አንቺም ነገርሽ ሁላ እንደሳቸው ነው። ደሞስ የሳቸው
ስም መቸ ኻፍሽ ጠፍቶ ያውቃል?”
ከት ብላ ስትስቅ እሱም ሳቀ።
“ስለ ትምርት ላወራህ ፈልጌ ነው የሳቸውን ስም ያነሳሁ” አለችው፣
ፈገግ ብላ። “በሳቸው ዘመን የተማሮች ቁጥር ኸዝኸ ኸደብረሥላሤ ስንኳ ብዙ ነበር ይላሉ። ስንክሳርም በብዛት የተጣፈው በሳቸው ግዝየ
ነው። እንደ ክፍለ ዮሐንስ የመሰሉ ሊቃውንትም ኸጎዣም ያመጡ
እሳቸው ናቸው። ሊቁ አዛዥ ከናፍሮም ቢሆኑ በሳቸው ግዝየ ነው የነበሩ። ዛዲያ ልነግርህ የፈለግሁት ቁስቋም ውስጥ ትምርት ቤት ማቆም ብቻ ሳይሆን፣ ለተማሮቹና ላስተማሮቹ ድጋፍ ማረግ አለብን
ሚለውን ነው።”
“እኔም ስለሱ ነግርሻለሁ እያልሁ ነበር። ሌላ ደሞ ባለፈው መጻሕፍት ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ እንዲመለሱ ፈልጋለሁ ስትይ
ማልነበር?”
"ትርጉም.... አዎ ስል ነበር። ሁሉ ባግባቡ ነው። ባለፈው መላከ
ጠሐይ ሮብዓምን ትርጉም ላይ ቢበረታ ብያቸው ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ሚመልሱ ሰዎች አምጥተው ሥራ እንዲዠምሩ ተደርጓል።
ለእነመላከ ጠሐይ ሃይማኖትን ሚያስተምረውንና ላገር ሚጠቅመውን ሁሉ እንዲያስተረጉሙ ነግሬያቸው እነሱ ተመካክረው ወስነዋል።”
"የትርጉም ሥራ ለገዳማቱ ቢሰጥ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቸ።”
“ዛዲያ ምን አለ... ይሰጣል ። በጎ አሳብ ነው። ትዛዝ ሰጣለሁ። እኔ
መቸም ቢሞላልኝ አገር ሁሉ መጻፍ በመጻፍ እንዲሆንና ትምርት
እንዲስፋፋ ነው ምፈልግ። እኔ ራሴም ብሆን አንድ ቀን ስለ እመቤታችን ማርያም ታምር አስጥፋለሁ ብየ አስባለሁ። ደሞ እሑድ እሑድ ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ግብር እናግባላቸው። አንተም ለነሱ ትልቅ ክብር አለህ። ቅኔም ተምረሀል። ቅኔ እውቀቴ እንዳንተ ባይሆንም፣ሊቃውንቱ ቅኔ ሲቀኙ ስሰማ መንፈሴ ሁሉ ይታደሳል። በተለይማ
የአክስትህን ልዥ እመት ወለተብርሃንን ስሰማ እንዳው እንደሳቸው ቅኔ በቻልሁ እላለሁ፡፡ አንተማ ኸኔም የበለጠ ትወዳቸዋለህ።”
የአክስቱ ልጅ ነገር ሲነሳ ፈገግ አለ። “ውነትሽ ነው እመት ወለተብርሃን ታላቅ የቅኔ ሊቅ ናቸው። እሑድ እሑድ ግብር ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ማግባት ያልሽው ተገቢ ነው። በተነጋገርነው መሠረትም በአካባቢው ወይን እንዲተከል ቦታ ብታስጠኚ። ቃሮዳ አየሩ ለወይን ተስማሚ ነው ሲሉ ሰምቻለሁ። ቅርብም ነው።”
“ውነትህ ነው። ዛሬውኑ ሰው ይላካል።”
ሁለቱም ዝም አሉ።
“ግና ካህናቱና ሊቃውንቱ... ምናለ ልብሳቸውን ቢያጠዱ?” አላት።
ያልጠበቀችው በመሆኑ ከት ብላ ሳቀች። “ልብሳቸውን እንዲያጥቡ
ማረግ ይቻላል ። በጐንደር ዙርያና በየገዳማቱ እንዶድ ኣስተክለን
ልብሳቸውን እንዲያጥቡ እናረጋለና” አለችው፣ አሁንም እየሳቀች።
“ዋናዎቹ ካህናት ደሞ የወርቅ ጫማ እንዲያረጉ ፈልጋለሁ።”
“ወርቅ አሳብ ነው። ይታዘዝላቸዋል። የአክብሮትህ ምልክት ነው።
እንደገና ዝም ብለው ተቀመጡ። ኢያሱ ሐሳብ የገባው ይመስላል።
እሷም ዝም ብላ ታየዋለች።
ዐይን ዐይኗን እያየ፣ “አደን ብኸድ ትፈቅጅልኛለሽ?” እናቱን ፈሪና
አክባሪ ነው።
ዕጢዋ ዱብ አለ። አፏ ተያዘ። ሊመጣበት የሚችለው አደጋ
አሳሰባት። ጥያቄው ግን አንድ ቀን እንደሚመጣ ታውቃለች።
“ኣባትህ ስንኳ በኸዱ ቁጥር እጨነቅ ነበር። ኢያሱ እንድትኸድ
አልፈልግም፤ ጭንቀቱን አልችለውም።”
“ምን ችግር አለው?”
“ባትኸድ መርጣለሁ። ኢያሱ አልጋውን እኮ ባየነቁራኛ ሚጠባበቅአለ!”
“ሁሉስ እያደኑ ማዶል እንዴ የኖሩት?”
“ገና ልዥ እኮ ነህ ኢያሱ።”
ድምጽዋ ተርበተበተ።
“አትጨነቂ። ምንም ሚመጣ ነገር የለም። ሰዎች ይዠ ነው ምኸደው
በዝኸ ላይ ደሞ አልቆይም።”
“ኻንተ መለየት አልፈቅድም ኢያሱ ... መቸ ትነሳለህ?”
ነገ።”
“ነገ?”
“አዎ! ነገ።”
“ታሰብህበት ቆይተሀል ማለት ነዋ! መቸስ ምን ኣረጋለሁ። ቁስቋም
ደሕና ትመልስህ። በጠሎቴ አልለይህም።”
አይዞሽ አትጨነቂ። በጠዋት ስለምኸድ ካሁኑ ልሰናበትሽ” አላት፣ጠዋት መጥቶ ቢሰናበታት እንባዋን ማየት ስለማይችል። ተነስታ ወደ እልፍኟ ስትሄድ በጭንቀት ተመለከታት።
በማግስቱ ጠዋት ከእናቷ ጋር በመስኮት ቆመው የአደን ዕቃው
በቅሎ ላይ ሲጫን አይተው ሆዳቸው ባባ። ኢያሱ ፈረሱ ቀርቦለት፡ በሹሩባው ዙርያ ነጭ ሻሽ አስሮ፣ ካባውን ደርቦ ከዐጀቡ ጋር ብቅ ሲል፣ የቤተመንግሥት ባለሟሉ፣ ወታደሩ፣ ጋሻ ጃግሬውና ሌላው ሰገደ።ምንትዋብና እናቷ ግን ሲቃ ያዛቸው።
ከቤተመንግሥት ግቢ ሲወጣ፣
ምንትዋብ ጩሂ ጩሂ አላት። እንኰዬ ትከሻዋን መታ መታ አደረጓት።እሳቸውም እንባ እንባ ብሏቸዋል፤ ግን እሷን ማረጋጋት መረጡ።
ሁለቱም በየክፍላቸው ገብተው ወገባቸውን በገመድ አስረው ሱባዔ ገቡ። መሬት ላይ ተኙ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ጸሎታቸው ሠምሮ ኢያሱ በሰላም ተመለሰ። እናትና ልጅ ገመድ ትጥቃቸውን ፈቱ።የነበሩበትን ጭንቀት ሳይናገሩ በደስታ ተቀበሉት።
እያደር የአደን ፍቅር በረታበት፤ መዝናኛው አደረገው። በሄደ ቁጥር
እናቱና አያቱ ወገባቸውን በገመድ ጠፍረው መሬት መተኛትና ሱባዔ
መግባት፣ ሲመጣ ደግሞ ገመዳቸውን ፈትተው መጣል፣ ጸማቸውን መፍታት ልማድ አደረጉት። እንደዚህ እያለም ኢያሱ የከፋ ነገር ሳይገጥመው ቀለል ያለ አደን ማካሄዱን ቀጠለ።
ከእናቱ ጋር በተስማሙት መሠረት ከንባብ ቤት እስከ ትርጓሜ ቤት
ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያምን በትምህርት ለማደራጀት ወጡ ወረዱ።ሁለት መቶ የሚጠጉ ምርጥ ሊቃውንት ከጐንደር ገዳማትና ከሌላ የሃገሪቱ ክፍሎች እየመጡ ወንበር ዘረጉ
የተማሪ ጎጆዎች ተቀለሱ። ትምህርት ከቁስቋም ሌላ በየገዳማቱና በየደብሮቹ ተስፋፋ። ወሬውን የሰማ ተማሪ ከየቦታው ፈልሶ ጐንደር ገባ፡፡ ጐንደር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ የሊቃውንት ማፍሪያና
መሰብሰቢያ ሆነች። ከጐንደር ውጭም ትምህርት ቤቶች ተስፋፉ።
የዜማ ሊቃውንት ድርጎ በማግኘታቸው ሙያቸውን አበለፀጉ ቤተክርስቲያንን አገለገሉ፤ ቤተመንግሥትንም አዝናኑ።
የሥዕል ሥራ በአያሌው አደገ። ቀለም አጠቃቀም ጥንት ከነበረው
ለውጥ አመጣ፣ የአቀራረብና የይዘት ለውጦች መጡ። ሠዓሊዎች ድጎማ እየተደረገላቸው አብያተ ክርስቲያናትን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አስጌጡ።
👍9
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“አንተ የሥዕል ንጉሥ ነህ።”
ጥላዬ፣ የአለቃ ሔኖክን አርባ አውጥቶ፣ የምንትዋብን ንግሥ በዐይኑ በብረቱ አይቶ ደብረ ወርቅ ከተመለሰ በኋላ፣ ከዐዲሱ መምህሩ ከአለቃ ግዕዛን ጋር ትምህሩቱን ቀጠለ።
ብራና እያስጌጠ የሚያገኘውን እህል ወይም አሞሌ ጨው ምግብ ለምታቀርብለት ኮማሪት.. እንጎች.. እየሰጠ፣ የዓመት ልብሱን እየለበሰ ትምህርቱን ተያያዘው። ሥነ-ስቅለትን ከሠራ በኋላ በሙያው ትልቅ ዕመርታ አሳየ። ስሙ በደብረ ወርቅ ብቻ ሳይሆን ዲማና ሌሎችም ቦታዎች ድረስ ተዛመተ።
ለምንትዋብ የላከላት ሥዕል ምን ዓይነት ስሜት እንዳሳደረባት
ለማወቅ እየሞከረ መልስ ስለማያገኝለት ነገሩን ይተወዋል። እነማይ መነኩሴው ዘንድ ሄዶ ሊጠይቃቸው ያስብና ስሙ በአካባቢው እየታወቀ
በመምጣቱ ከመሄድ ይቆጠባል ።
በትምህርቱ ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለበት ወስኖ ወደሚቀጥለውና
የመመረቂያ ሥራው ወደሆነው ትኩረቱን አደረገ።
“እንግዲህ እስታሁን የሣልኻቸው በሙሉ ፍጡራን ናቸው። አሁን
አንድ ቀን፣ አለቃ ግዕዛን ቤት ተቀምጠው ሲጫወቱ፣ አለቃ ግዕዛን፣የፍጡራን ሁሉ ፈጣሪ የሆነውን አምላካችንን... አጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሤን - የኃያላኑ መቀመጫ የሆነውን - መንበረ ፀባኦትን መሣያ ግዝየህ ነው” አሉና፣ ባለቤታቸው ባፈና እንዲሰሙት ያልፈለጉትን ነገር
ለመናገር እጁን ይዘው ወደ ውጭ ወጡ።
ወደ ጥላዬ ዞረው፣ “የሥላሤ ምሥጢር ሴትና ምሥጢሩን ማወቅ የሌለበት ሰው ፊት አይወራም። ሥላሤ ምሥጢራቸው ጥልቅ፣ ሐሳቡ
ረቂቅ ስለሆነ ነው። ይኸ አሁን ምትሥለውና የመጨረሻ የሆነው፣
ከሁሉም ሚከብደውና ለመሣልም ጥንቃቄ ሚጠይቀው ሥራ ነው.
ምሥጢሩም ጥልቅ፣ ሐሳቡም ረቂቅ ነውና” አሉት።
“ሦስት አካል በአንድ አምሳል፣ ያለ ምንም ልዩነት መሣሉ ነው?
ሲል ጠየቀ፣ ከተቀመጠበት ተነሥቶ።
“ኣየ... እሱማ ተስተውሎ ይሠራል።”
“ዛዲያ ምኑ ነው ሚከብድ?”
“የሥላሴን ሥዕል ኣይተኻል?”
“ኣብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሉ?”
“አድምጠኝና ልንገርህ። ሥላሤ ሚሣሉበት ሠሌዳ ዐራት ማዕዘን
ይሆንና በዐራቱም የማዕዘኖች መገናኛ ላይ ሌሎች ዐራት እኩል
ማዕዘኖች ይሠመራሉ። ስምንት አልሆኑም?”
ጥላዬ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ።
“የሥላሤ በስምንት ማዕዘን መሣል ሚያመለክትህ፣ አንደኛ የስምንቱ
የሰማይ መስኮቶች ምሳሌ መሆናቸው፣ ሁለተኛ የዓለም ቅርፅ ይዘው በክብ እኩል ማዕዘን ውስጥ መቀመጣቸው ሲሆን ሦስተኛ በተመሳሳይ መልክ መሣላቸው ነው። በስምንቱ መስመሮቹ ውስጥ፣ የሰው፣ የአንበሳ፡ የላምና የንስር ምስሎች ይሣላሉ። አየህ ያልተመራመረ ተመልካች እነዝኸን በየማዕዘኑ የተሣሉ ዐራት ፍጡራን ምንነት ብትጠይቀው ዐራቱ ወንጌላውያን ናቸው ብሎ ይመልስልህና ያልፋል።”
“ዛዲያ የምንድር ናቸው?”
“አትቸኩል ላስረዳህ ነው። አየህ የነሱን ምንነት ለመገንዘብ
በመዠመሪያ በእኩል ነጥብ መኻል ላይ ከሚይዙት ክብ ነገር መዠመር አለብህ። ከክቡ ተነስተህ ደሞ ወደ ስምንቱም አቅጣጫ ብታሰምር፣ ሚከተለውን ክብ ንድፍ ታገኛለህ” ኣሉት፣ መሬት ላይ በስንጥር ክብ
ቅርፅ ሰርተውና በክቡ ቅርፅ ውስጥ ስምንት መስመሮች አስምረው።
ጥላዬ፣ ራሱን እየነቀነቀ የሚሥሉትን ይመለከታል።
“እንግዲህ የክቡ ትርጓሜ ዓለም በመዳፋቸው ላይ መሆኗ ነው።
ክብ የዓለማችን ቅርጥ መሆኑንና የዓለማችን ፈጣሪም መዠመሪያውም ፍጻሜውም የማይታወቀው የኅያው እዝጊሃር ምሥጢር ነው። አሁን
ዐውደ ዓመት በዐራቱ ወንጌላውያን ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ እየተመሰለ በየዐራት ዓመቱ ይመላለሳል አዶለም? በነገራችን ላይ
ማቴዎስ በሰው፣ ማርቆስ በአንበሳ፣ ሉቃስ በላም ሲመሰሉ ዮሐንስ ደሞ በንስር ይመሰላል። ይኸም ምሳሌ በዘፈቀደ የተሰጠ እንዳይመስልኸ።
የየወንጌላቸው አካኼድ ተጠንቶ ነው ይኸ ምሳሌ መሰጠቱ። እንዲያው ለአብነት ብናይ ማቴዎስ በሰው መመሰሉ 'አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፣
ይስሐቅ ያዕቆብን እያለ የክርስቶስን ሰዋዊ የዘር ሐረግ በመዘርዘር ስለሚጀምር ነው። ዮሐንስም ንሥር መባሉ 'ዘልዑለ ይሠርር' ይለዋል ከፍ ብሎ የሚበር በመኾኑ።
ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ በመጀመሪያ
ቃል ነበረ ብሎ የመጠቀ አሳብ በማምጣቱ ነው። ማርቆስና ሉቃስም የየራሳቸው ትርጓሜ አላቸው፤ መጣፉን ተመልከተው። እና ዐውድ ማለት ክብ ማለት ነው። የክቡ መኻል የብርሃን መገኛ ምንጭ ነው ጠሐይ ማለት ነው። ጠሐይ ሙቀት አላት ማዶል? ሙቀቱ እንግዲህ
አብ ነው። አካሉ ደሞ ወልድ ነው... ጠሐይ አካል ማዶለች? ብርሃኑ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ጠሐይ ብርሃን እንዳላት ሁሉ። እና እኼን ሁሉ አውቀህና ተረድተህ ነው ሥላሤን መሣል ምትችለው። ደሞም በሥላሤ ራስ ላይ እግረ ፀሐይ ትሥላለኸ፤ የብርሃን ክበብ ነው። ዛዲያ ሥላሤ ብቻ ሳይኾኑ ቅዱሳን ኹሉ እግረ ፀሐይ በአናታቸው ዙሪያ ሳይደረግ
አይሣሉም። ለምን ቢሉ የሥላሤ ብርሃን ያረፈባቸው፤ መንፈስ ቅዱስ የዋጃቸው መኾኑን ማሳያችን፣ ኸጥንት የነበረ ትውፊታችን ነው።”
“ይኸ ራሱ ነገሩን ያከብደዋል።”
“ሥላሤ አንድም ሦስትም ስለሆኑ በተመሳሳይ ምንገድ ይሣላሉ።
በተመሳሳይ ምንገድ መሣላቸው ደሞ ቅድም እንዳልሁህ የፍጹም
አንድነታቸው ማሳያ ነው። ስለዝኸ የተለያዩ ገጥታዎችን አንድ ገጥታ
ሰጥተህ ነው ምትሥላቸው።”
“ተረድቻለሁ።”
“መልካም... ሥላሤን ስትሥል ግራም ቀኝም፣ ኸላይም ኸታችም
እኩል ማረግ አለብህ። ምትሥልበትን ቦታ ጭምር አመጣጥነህ ነው ምትሥል። እነሱ ጉድለት የለባቸውምና ምንም ዓይነት እንከን ሳይኖርባቸው... ምንም ዓይነት ጉድለት ሳታሳይ... ሳታዛንፍ ነው መሣል ያለብህ። አንዱን ከፍ ሌላውን ዝቅ ማረግ አይቻልም። ፊታቸው ላይ
ሚታየውንም ገጥታ አንድ ማረግ ያስፈልጋል። ይኸን ሁሉ ስታውቅ፡
ችሎታህ ሲዳብር ነው፣ ቤተክሲያን ውስጥ መሣል ሚፈቀድልህ።፥
“እህ...”
“አዎ እንደሱ ነው ደንቡ።"
ከዚያ በኋላ፣ ጥላዬ ንባብ ላይ ተጠመደ፡፡ አለቃ ግዕዛን በአስተማሩት ላይ ተጨማሪ ንባብ አደረገ፤ ብራናዎችን አገላበጠ፤ ከሊቃውንት ጋር ተቀምጦ ተወያየ።
አለቃ ግዕዛን ሥላሤን ለመሣል በቂ እውቀት አከማችቷል ብለው
ሲያስቡ ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብቶ እንዲስል ፈቀዱለት።
የመጨሻዎቹ ቀናት ቤቱ ውስጥ በር ዘግቶ ጾምና ጸሎት ያዘ። ተንበርክኮ፣ “አምላኬ ሆይ፣ ማደርያህ የሆነችው ቤተክርስቲያንህ ውስጥ ገብቸ መዐዛቸው ዕጣን ሳይሆን ወንጌል የሆነውን ሥላሤን መሣያ ግዝዬ ስለደረሰ ጥበብን ስጠኝ። መልካቸውን ግለጥልኝ። አንተ አበርታኝ”ሲል አምላኩን ተማጸነ። በረከት ይሆነው ዘንድ የቅዱሳንን ገድል እንዲሁም ወንጌልን እየደጋገመ አነበበ።
ከሦስት ተከታታይ ሱባኤያት በኋላ፣ እሑድ ቀን ሥጋ ወደሙን
ተቀበለ። ሰኞ ጠዋት፣ ከእንቅልፉ ሲነቃ የፀሐይ ጨረር በበሩ ቀዳዳ
ገብታለች። የረፈደበት መስሎት ሥላሤ ፊት መቅረቢያ ሰዐቱ ስለደረሰ ተጣጠበ። የክት ልብሱን ለብሶ፣ ራሱ ላይ እንደወተት የነጣ ጥምጥም አድርጎ፣ በባዶ ሆዱ፣ ደጅ ሲወጣ ፀሐይቱ ሞቅ ብላለች። ብርሃኗ ዐይን
ያጥበረብራል። ሰማዩ ጥርት ብሏል።
ደስ ደስ አለው። የሰማዩ ጥራት ማረከው። ፀሐይቱና ሰማዩ የዛሬ
ውሎው የተቃና እንደሚሆንለት ቃል ኪዳን የገቡለት መሰለው።
መንፈሱን አበረቱት። በዚያች ቀን በሕይወት መኖሩም አስደሰተው።
አቤቱ አምላኬ! ይችን ቀን ስላሳየኸኝ ከልቤ አመሰግንሀለሁ። የዛሬ
ሥራየንም እንደዝች ጠሐይ የበራ እንደዝኸ ሰማይ የጠራ አድርግልኝ
ኣለ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“አንተ የሥዕል ንጉሥ ነህ።”
ጥላዬ፣ የአለቃ ሔኖክን አርባ አውጥቶ፣ የምንትዋብን ንግሥ በዐይኑ በብረቱ አይቶ ደብረ ወርቅ ከተመለሰ በኋላ፣ ከዐዲሱ መምህሩ ከአለቃ ግዕዛን ጋር ትምህሩቱን ቀጠለ።
ብራና እያስጌጠ የሚያገኘውን እህል ወይም አሞሌ ጨው ምግብ ለምታቀርብለት ኮማሪት.. እንጎች.. እየሰጠ፣ የዓመት ልብሱን እየለበሰ ትምህርቱን ተያያዘው። ሥነ-ስቅለትን ከሠራ በኋላ በሙያው ትልቅ ዕመርታ አሳየ። ስሙ በደብረ ወርቅ ብቻ ሳይሆን ዲማና ሌሎችም ቦታዎች ድረስ ተዛመተ።
ለምንትዋብ የላከላት ሥዕል ምን ዓይነት ስሜት እንዳሳደረባት
ለማወቅ እየሞከረ መልስ ስለማያገኝለት ነገሩን ይተወዋል። እነማይ መነኩሴው ዘንድ ሄዶ ሊጠይቃቸው ያስብና ስሙ በአካባቢው እየታወቀ
በመምጣቱ ከመሄድ ይቆጠባል ።
በትምህርቱ ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለበት ወስኖ ወደሚቀጥለውና
የመመረቂያ ሥራው ወደሆነው ትኩረቱን አደረገ።
“እንግዲህ እስታሁን የሣልኻቸው በሙሉ ፍጡራን ናቸው። አሁን
አንድ ቀን፣ አለቃ ግዕዛን ቤት ተቀምጠው ሲጫወቱ፣ አለቃ ግዕዛን፣የፍጡራን ሁሉ ፈጣሪ የሆነውን አምላካችንን... አጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሤን - የኃያላኑ መቀመጫ የሆነውን - መንበረ ፀባኦትን መሣያ ግዝየህ ነው” አሉና፣ ባለቤታቸው ባፈና እንዲሰሙት ያልፈለጉትን ነገር
ለመናገር እጁን ይዘው ወደ ውጭ ወጡ።
ወደ ጥላዬ ዞረው፣ “የሥላሤ ምሥጢር ሴትና ምሥጢሩን ማወቅ የሌለበት ሰው ፊት አይወራም። ሥላሤ ምሥጢራቸው ጥልቅ፣ ሐሳቡ
ረቂቅ ስለሆነ ነው። ይኸ አሁን ምትሥለውና የመጨረሻ የሆነው፣
ከሁሉም ሚከብደውና ለመሣልም ጥንቃቄ ሚጠይቀው ሥራ ነው.
ምሥጢሩም ጥልቅ፣ ሐሳቡም ረቂቅ ነውና” አሉት።
“ሦስት አካል በአንድ አምሳል፣ ያለ ምንም ልዩነት መሣሉ ነው?
ሲል ጠየቀ፣ ከተቀመጠበት ተነሥቶ።
“ኣየ... እሱማ ተስተውሎ ይሠራል።”
“ዛዲያ ምኑ ነው ሚከብድ?”
“የሥላሴን ሥዕል ኣይተኻል?”
“ኣብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንደሚሉ?”
“አድምጠኝና ልንገርህ። ሥላሤ ሚሣሉበት ሠሌዳ ዐራት ማዕዘን
ይሆንና በዐራቱም የማዕዘኖች መገናኛ ላይ ሌሎች ዐራት እኩል
ማዕዘኖች ይሠመራሉ። ስምንት አልሆኑም?”
ጥላዬ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ።
“የሥላሤ በስምንት ማዕዘን መሣል ሚያመለክትህ፣ አንደኛ የስምንቱ
የሰማይ መስኮቶች ምሳሌ መሆናቸው፣ ሁለተኛ የዓለም ቅርፅ ይዘው በክብ እኩል ማዕዘን ውስጥ መቀመጣቸው ሲሆን ሦስተኛ በተመሳሳይ መልክ መሣላቸው ነው። በስምንቱ መስመሮቹ ውስጥ፣ የሰው፣ የአንበሳ፡ የላምና የንስር ምስሎች ይሣላሉ። አየህ ያልተመራመረ ተመልካች እነዝኸን በየማዕዘኑ የተሣሉ ዐራት ፍጡራን ምንነት ብትጠይቀው ዐራቱ ወንጌላውያን ናቸው ብሎ ይመልስልህና ያልፋል።”
“ዛዲያ የምንድር ናቸው?”
“አትቸኩል ላስረዳህ ነው። አየህ የነሱን ምንነት ለመገንዘብ
በመዠመሪያ በእኩል ነጥብ መኻል ላይ ከሚይዙት ክብ ነገር መዠመር አለብህ። ከክቡ ተነስተህ ደሞ ወደ ስምንቱም አቅጣጫ ብታሰምር፣ ሚከተለውን ክብ ንድፍ ታገኛለህ” ኣሉት፣ መሬት ላይ በስንጥር ክብ
ቅርፅ ሰርተውና በክቡ ቅርፅ ውስጥ ስምንት መስመሮች አስምረው።
ጥላዬ፣ ራሱን እየነቀነቀ የሚሥሉትን ይመለከታል።
“እንግዲህ የክቡ ትርጓሜ ዓለም በመዳፋቸው ላይ መሆኗ ነው።
ክብ የዓለማችን ቅርጥ መሆኑንና የዓለማችን ፈጣሪም መዠመሪያውም ፍጻሜውም የማይታወቀው የኅያው እዝጊሃር ምሥጢር ነው። አሁን
ዐውደ ዓመት በዐራቱ ወንጌላውያን ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ እየተመሰለ በየዐራት ዓመቱ ይመላለሳል አዶለም? በነገራችን ላይ
ማቴዎስ በሰው፣ ማርቆስ በአንበሳ፣ ሉቃስ በላም ሲመሰሉ ዮሐንስ ደሞ በንስር ይመሰላል። ይኸም ምሳሌ በዘፈቀደ የተሰጠ እንዳይመስልኸ።
የየወንጌላቸው አካኼድ ተጠንቶ ነው ይኸ ምሳሌ መሰጠቱ። እንዲያው ለአብነት ብናይ ማቴዎስ በሰው መመሰሉ 'አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፣
ይስሐቅ ያዕቆብን እያለ የክርስቶስን ሰዋዊ የዘር ሐረግ በመዘርዘር ስለሚጀምር ነው። ዮሐንስም ንሥር መባሉ 'ዘልዑለ ይሠርር' ይለዋል ከፍ ብሎ የሚበር በመኾኑ።
ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ በመጀመሪያ
ቃል ነበረ ብሎ የመጠቀ አሳብ በማምጣቱ ነው። ማርቆስና ሉቃስም የየራሳቸው ትርጓሜ አላቸው፤ መጣፉን ተመልከተው። እና ዐውድ ማለት ክብ ማለት ነው። የክቡ መኻል የብርሃን መገኛ ምንጭ ነው ጠሐይ ማለት ነው። ጠሐይ ሙቀት አላት ማዶል? ሙቀቱ እንግዲህ
አብ ነው። አካሉ ደሞ ወልድ ነው... ጠሐይ አካል ማዶለች? ብርሃኑ መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ጠሐይ ብርሃን እንዳላት ሁሉ። እና እኼን ሁሉ አውቀህና ተረድተህ ነው ሥላሤን መሣል ምትችለው። ደሞም በሥላሤ ራስ ላይ እግረ ፀሐይ ትሥላለኸ፤ የብርሃን ክበብ ነው። ዛዲያ ሥላሤ ብቻ ሳይኾኑ ቅዱሳን ኹሉ እግረ ፀሐይ በአናታቸው ዙሪያ ሳይደረግ
አይሣሉም። ለምን ቢሉ የሥላሤ ብርሃን ያረፈባቸው፤ መንፈስ ቅዱስ የዋጃቸው መኾኑን ማሳያችን፣ ኸጥንት የነበረ ትውፊታችን ነው።”
“ይኸ ራሱ ነገሩን ያከብደዋል።”
“ሥላሤ አንድም ሦስትም ስለሆኑ በተመሳሳይ ምንገድ ይሣላሉ።
በተመሳሳይ ምንገድ መሣላቸው ደሞ ቅድም እንዳልሁህ የፍጹም
አንድነታቸው ማሳያ ነው። ስለዝኸ የተለያዩ ገጥታዎችን አንድ ገጥታ
ሰጥተህ ነው ምትሥላቸው።”
“ተረድቻለሁ።”
“መልካም... ሥላሤን ስትሥል ግራም ቀኝም፣ ኸላይም ኸታችም
እኩል ማረግ አለብህ። ምትሥልበትን ቦታ ጭምር አመጣጥነህ ነው ምትሥል። እነሱ ጉድለት የለባቸውምና ምንም ዓይነት እንከን ሳይኖርባቸው... ምንም ዓይነት ጉድለት ሳታሳይ... ሳታዛንፍ ነው መሣል ያለብህ። አንዱን ከፍ ሌላውን ዝቅ ማረግ አይቻልም። ፊታቸው ላይ
ሚታየውንም ገጥታ አንድ ማረግ ያስፈልጋል። ይኸን ሁሉ ስታውቅ፡
ችሎታህ ሲዳብር ነው፣ ቤተክሲያን ውስጥ መሣል ሚፈቀድልህ።፥
“እህ...”
“አዎ እንደሱ ነው ደንቡ።"
ከዚያ በኋላ፣ ጥላዬ ንባብ ላይ ተጠመደ፡፡ አለቃ ግዕዛን በአስተማሩት ላይ ተጨማሪ ንባብ አደረገ፤ ብራናዎችን አገላበጠ፤ ከሊቃውንት ጋር ተቀምጦ ተወያየ።
አለቃ ግዕዛን ሥላሤን ለመሣል በቂ እውቀት አከማችቷል ብለው
ሲያስቡ ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብቶ እንዲስል ፈቀዱለት።
የመጨሻዎቹ ቀናት ቤቱ ውስጥ በር ዘግቶ ጾምና ጸሎት ያዘ። ተንበርክኮ፣ “አምላኬ ሆይ፣ ማደርያህ የሆነችው ቤተክርስቲያንህ ውስጥ ገብቸ መዐዛቸው ዕጣን ሳይሆን ወንጌል የሆነውን ሥላሤን መሣያ ግዝዬ ስለደረሰ ጥበብን ስጠኝ። መልካቸውን ግለጥልኝ። አንተ አበርታኝ”ሲል አምላኩን ተማጸነ። በረከት ይሆነው ዘንድ የቅዱሳንን ገድል እንዲሁም ወንጌልን እየደጋገመ አነበበ።
ከሦስት ተከታታይ ሱባኤያት በኋላ፣ እሑድ ቀን ሥጋ ወደሙን
ተቀበለ። ሰኞ ጠዋት፣ ከእንቅልፉ ሲነቃ የፀሐይ ጨረር በበሩ ቀዳዳ
ገብታለች። የረፈደበት መስሎት ሥላሤ ፊት መቅረቢያ ሰዐቱ ስለደረሰ ተጣጠበ። የክት ልብሱን ለብሶ፣ ራሱ ላይ እንደወተት የነጣ ጥምጥም አድርጎ፣ በባዶ ሆዱ፣ ደጅ ሲወጣ ፀሐይቱ ሞቅ ብላለች። ብርሃኗ ዐይን
ያጥበረብራል። ሰማዩ ጥርት ብሏል።
ደስ ደስ አለው። የሰማዩ ጥራት ማረከው። ፀሐይቱና ሰማዩ የዛሬ
ውሎው የተቃና እንደሚሆንለት ቃል ኪዳን የገቡለት መሰለው።
መንፈሱን አበረቱት። በዚያች ቀን በሕይወት መኖሩም አስደሰተው።
አቤቱ አምላኬ! ይችን ቀን ስላሳየኸኝ ከልቤ አመሰግንሀለሁ። የዛሬ
ሥራየንም እንደዝች ጠሐይ የበራ እንደዝኸ ሰማይ የጠራ አድርግልኝ
ኣለ።
👍13❤4
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ሰሞኑን ቀለሞቹ ከደረቁለት በኋላ፣ እየተመላለሰ ሲቀባ፣ ሲያስተካክል፣ ሲያበጃጅና ሲሞሽር ቆይቶ ከአምስት ቀናት ድካምና ጥንቃቄ የተሞላው
ሥራ በኋላ፣ ሦስቱን ሥላሤ ሥሎ ጨረሰ። የመጨረሻው ቀን ራቅ
ብሎ ሥዕሉን ሲመለከት ተደነቀ። ሦስቱም በሁሉም አቅጣጫ እኩልና የተመጣጠኑ ናቸው። አንድም የተዛነፈና ከቦታው ውጭ የሆነ ነገር የለም። የፊታቸው ገፅታ ፍፁም ተመሳሳይ ነው። ፊታቸው ሙሉ ለሙሉ ይታያል። በሰማያዊ፣ በቢጫ፣ በነጭና በቀይ ቀለማት አምረዋል።
ተንበርክኮ ምስጋና አቅርቦ ወጣ።
በማግስቱ፣ አለቃ ግዕዛን ከሊቀጠበብት አዳሙ፣ ከአለቃ ተክለየሱስና ከሊቀጠበብት ያሬድ ጋር መጥተው ሥዕሉን ተመለከቱ። ጥላዬ፣ከኋላቸው ቆሞ፣ በእነዚህ ታላላቅ ሠዓሊዎችና የሥዕል መምህራን ላይ ያሳደረውን ስሜት ለማወቅ ተጠባበቀ።
መምህራኑ ፈዘው ተመለከቱ፤ የሚያዩትን ማመን አቃታቸው።
አለቃ ግዕዛን፣ “ጥላዬ፣ ይኸ የፍቅር ውጤት ነው። ፍቅር ብቻ ነው ይኸን የመሰለ ሥራ ሊያሠራ ሚችለው። እስታሁን በሥራህ ደስተኛ ነበርሁ። ዛሬ ግን ይኸን የመሰለ የላቀ ሥራ ስላሳየኸኝ አከብርሃለሁ።
ይኸን የመሰለ የጥበብ ውጤት እንዳይ ዕድሜ ለሰጡኝ ሥላሤ ምስጋናዬን ሳቀርብ፣ ላንተ ደግሞ አድናቆቴን ገልጣለሁ። አንተም ሥላሤን ብቻ ሳይሆን እኔንም ነው ያከበርኸኝ። እኔን እንዳከበርኸኝ አንተን ደሞ ሥላሤ ያክብሩህ። አንተ የሥዕል ንጉሥ ነህ። ከይኸ ቀደም ማንም አልቀደመህም፣ አሁንም ሚደርስብህ የለም ወደፊትም ሚተካህ ዠግና
ሚመጣበት ግዝየ ሩቅ ነው” አሉት፣ ደብቀውና ተጠንቅቀው የያዙትን፣ለማንም ተማሪ አድረገውት የማያውቁትን ምስጋና እያዘነቡለት።
ጥላዬ እግዚሐር ይስጥልኝ ማለት ፈልጎ፣ ልሳኑ ተዘጋበት። በዝምታ
እግራቸው ሥር ተደፋ።
“ተነስ ልዥ ። ንጉሥ እሰው እግር ሥር ኣይወድቅም” አሉት።
ሊቀጠበብት አዳሙም፣ “ውነትም የሥዕል ንጉሥ ነህ። አንተ ዛሬ
ግዕዛንን ብቻ ሳይሆን ሁላችንንም ነው ያከበርኸው፣ ያኮራኸው። ውበት ማለት ይኸ እንጂ ሌላ ምን አለ? አንተ ለብዙ ተማሮች አርአያ
ትሆናለህ። ሚያሳዝነው ሥዕል እንደዝኸ ድንቅ ነገር ሁኖ ሳለ እንደ ቅኔና ዜማ በርካታ ተማሮች የሉትም። ደብረ ወርቅ እንደመጣህና ትምርት እኔጋ እንደዠመርህ፣ ውነትም የሥዕል ንጉሥ እንደምትሆን አውቄ ነበር። የናትህ ማጠን ይለምልም። ዛሬ የአለቃ ሔኖክ ነፍስም በሰማይ ቤት ትዘምራለች። ሥላሤ እጅህን ያለምልሙት” ብለው
ሊስሙት ሲጠጉት፣ ፈጠን ብሎ እግራቸውን ሳመ።
አለቃ ተክለየሱስና ሊቀጠበብት ያሬድም አድናቆትና ምስጋና
አዥጎድጎዱለት፤ ባረኩት፤ እንኳን ደስ ያለህ ብለው ሳሙት። እሱም
እግራቸውን ሳመ።
በምስክር ፊት በሥዕል ትምህርት ተመረቀ።
የመመረቂያውን አነስተኛ ድግስ እንዲቀምሱለት ሁሉንም ወደቤቱ
ይዟቸው ሄደ። እንጎች ያዘጋጀችውን ምግብ በልተው፣ አረቄ ጠጥተው አመስግነውትና መርቀውት ሊሄዱ ሲሉ፣ ሊቀጠበብት ያሬድ በድንገት
ሲቆሙ፣ ሌሎቹም ቆሙ።
ሁሉንም በተራ እየተመለከቱ፣ “በሉ ወንድሞቼ ኸመኼዳችን
በፊት አንድ ቅር ያለኝን ጉዳይ ልናገር ነው” አሉ። “ተማሪ እናታባቱ ያወጡለትን ስም እየተወ ለራሱ ስም ያወጣል። ዜማ ሲማር 'ጥዑመ ልሳን ነኝ ይላል። ቅኔ ሲማር ባሕረ ጥበብ ነኝ... ማንቴስ ነኝ ይላል።አንዳንዴም እሰበሱ ስም ይሸላለማል። ይኸ ልዣችን ግን ትሑትና የሥራ ሰው በመኾኑ ይኸው የባላገር ስሙን እንደያዘ ጥላዬ እንደተባለ
አለ። ምሥጢሩ ደግ ነው፤ ጥላ ከለላ ትኾነኛለኽ ሲሉ ማዶል አባቱ
“ጥላዬ ማለታቸው? ድንቅ ስም ነው። ግና ለእንዳንተ ያለ ጠቢብ
ዛሬ እናንተ ወንድሞቼ ኸፈቀዳችኹልኝ 'ሥሙር' ብዬዋለኹ። ደሞም አይኾንም። ሠዓሊ ተኹኖ ጥላዬ መባል ምሥጢሩ አይገጥምም። ስለዚኸ
ፊቱኑ የነበረ ወግ ነው። መምህራን ለጥበብ ልዦቻቸው ይስማማል
ያሉትን ስም ይሽልማሉ። እና ምን ትላላችኹ? ሥሙር አይዶለም
ጥላዬ?”
ሁለቱም መምህራን በአንድ ድምጽ በደስታ አደነቁት፣ “ቃለ ሕይወት ያሰማዎ ጌታዬ፤ ድንቅ ነው፤ ሥሙር ነው፤ ስሙም አሰያየሙም የተገባ ነው” ብለው አጸኑለት።”
መምህሮቹ በደስታ እያውካኩ ሲሄዱ ሸኝቷቸው እንደተመለሰ መደብ ላይ ጋደም አለ። የተዋጣለት ሥራ እንደሠራ አረጋገጠ። ሕልሙ ሁሉ
እውን ሆነ። ቋራ እያለ ወለቴን ንጉሥ ኸወሰዳት እኔ የሥዕል ንጉሥ ማልሆን? ያለውን አስታወሰ።ምኞቱ ሠመረ።
ዝናው በደብረ ወርቅ ብቻ ሳይሆን፣ አድባራቱን አልፎ መርጡለማርያም ድረስ ዘለቀ። በየደብሩ ያሉት የሥዕል መምህራን እንዲያስተምር
ገፋፉት። ዝናውን የሰሙ የአካባቢው ባላባቶች ደብራቸውን እንዲያስጌጥ ተረባረቡበት።
እሱ ግን አንዴ ለአንዱ ባላባት አድሮ መሥራት ከጀመረ ወደሌላው መሄድ ስለማይችል ለማንም አልታዘዝ አለ። በተጨማሪ፣ ሥዕል ታሪክ
ተናጋሪ፣ አስተማሪ፣ አብራሪ፣ ስሜትንና አእምሮን ቀስቃሽ እንጂ ለስም መጠሪያ ቤተክርስቲያን ማስዋቢያ ብቻ ሆኖ መወሰድ እንደሌለበት ተናገረ። በባላባቱ ዘንድ ቅሬታን አተረፈ።
ጐንደር ተመልሶ መሄድ ፈልጎ ከሀያ ዓመት በላይ በመቆየቱ
ባይተዋር የሚሆን መሰለው። ጐንደርን እንደዛ ወዶ ይህን ያህል
ርቆ መቀመጡ አልገባ አለው። ደብረ ወርቅ ብዙ አስተምራዋለች።
በርግጥም የሥዕል ንጉሥ አድርጋዋለች። ሆኖም ደብረ ወርቅ
የሕዝብ ዓይነት አይታይባትም። ደብረ ወርቅ ነዋሪዎቿን
የጐንደርን ዓይነት ታላቅነትና ግርማ ሞገስ የላትም። እንደ ጐንደር አድርጋ የመቀመጥ ባህርይ ሲኖራት፣ ጐንደር አደባባይ አውጥታ ታሟግታቸዋለች፤ የቤተክርስቲያን ምርጫ ትሰጣቸዋለች፣ ለድሆቿ
የእንፋሎት መታጠቢያ እንኳን አዘጋጅታለች።
ታዲያ ይህችን ጐንደርን እንዴት አድርጎ ለዘላለም ይተዋት? እንደ
ወለቴ የልጅነት ፍቅሩ፣ የጎልማሳ ዘመኑ ትዝታው አይደለችምን?
ጐንደር ለመሄድ ባሰበ ቁጥር፣ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር
ወዳጅነት ያዙ” የሚለውን ወሬ መርሳት ስላልቻለ ልቡ ያመነታል።
ባሏ ከሞቱ ጊዜ የቀድሞው ስሜቱ አንሰራርቶ የነበረው ዜናውን
ሲሰማ ልቡ ተሰርጉዶ ምንትዋብ ላይ ቅሬታ አድሮበታል።
በምንትዋብ ቅር መሰኘቱ ቅር የሚያሰኘው አልፎ አልፎ ደግሞ
የሚያስቀው ነገር ሆኖ አግኝቶታል ቅሬታው የመነጨው እኔ ይህን
ያህል ስለእሷ ሳስብ እሷ እንዴት ሳታስፈልገኝ ቀረች በሚል ነው።
የሚያስበው ሁሉ ተገቢ እንዳልሆነ ቢያውቅም፣ “ውነት ትወደኝ ኸነበረ እንዴት አታስፈልገኝም?” ብሎ ደግሞ በስጨት ይላል። በሌላ በኩል አፄ በካፋ ሲሞቱ ልቡ ውስጥ የተስፋ ጭላንጭል የተቀረፀበትን ጊዜ ያስብና ከት ብሎ ይስቃል። ድጋሚ ሌላ ሥዕል ሊልክላት ወሰነ።ሆኖም እንደመነኩሴው ታማኝ ሰው እንዴትና የት እንደሚያገኝ ማሰብ
አቃተው።
ቀደም ብሎ ስለአብርሃ ወሬ ይሰማ የነበረውን ያህል ባለመስማቱም በሕይወት ይኖር ይሆን እያለ መጨነቁም አልቀረም። ካንድ ሁለት
ጊዜ መልዕክት ልኮበት ሳይደርሰው ቀርቶ ይሁን ወይንም ደርሶት ዝም ብሎት እንደሆነ ለማወቅ ተቸገረ።
አንድ ቀን፣ ደብረ ወርቅ ማርያም ውስጥ የቅኔ መምህር ከሆኑት
ከመጋቤ ሥነ-ጊዮርጊስ ጋር ቤተክርስቲያኗ ግቢ ውስጥ ያለ ጥድ ስር ተቀምጠው ሲጨዋወቱ በቅርቡ ጐንደር ሄደው እንደነበር ነገሩት።
“እደብረብርሃን ሥላሤ ደርሰው ነበር?” አላቸው።
“አዎን።”
“እንዲያው መጋቤ አብርሃ ሚባል ጓደኛ ነበረኝ። መልክትም
ብልክበት አልደረሰው ሁኖ ነው መሰለኝ መልስም አልሰጠኝ።”
“አሉ። መቸም ጐንደር ኻፈራቻቸው ሊቃውንት አንዱ ናቸው ነው ሚሉ።”
ጥላዬ ደስ አለው። ጐንደር የመሄድ ፍላጎቱ ተነሳሳ።
“እንዴት ያለ ጥሩ ነገር ነገሩኝ። እኔማ ተጨንቄ ቆይቻ።”
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ሰሞኑን ቀለሞቹ ከደረቁለት በኋላ፣ እየተመላለሰ ሲቀባ፣ ሲያስተካክል፣ ሲያበጃጅና ሲሞሽር ቆይቶ ከአምስት ቀናት ድካምና ጥንቃቄ የተሞላው
ሥራ በኋላ፣ ሦስቱን ሥላሤ ሥሎ ጨረሰ። የመጨረሻው ቀን ራቅ
ብሎ ሥዕሉን ሲመለከት ተደነቀ። ሦስቱም በሁሉም አቅጣጫ እኩልና የተመጣጠኑ ናቸው። አንድም የተዛነፈና ከቦታው ውጭ የሆነ ነገር የለም። የፊታቸው ገፅታ ፍፁም ተመሳሳይ ነው። ፊታቸው ሙሉ ለሙሉ ይታያል። በሰማያዊ፣ በቢጫ፣ በነጭና በቀይ ቀለማት አምረዋል።
ተንበርክኮ ምስጋና አቅርቦ ወጣ።
በማግስቱ፣ አለቃ ግዕዛን ከሊቀጠበብት አዳሙ፣ ከአለቃ ተክለየሱስና ከሊቀጠበብት ያሬድ ጋር መጥተው ሥዕሉን ተመለከቱ። ጥላዬ፣ከኋላቸው ቆሞ፣ በእነዚህ ታላላቅ ሠዓሊዎችና የሥዕል መምህራን ላይ ያሳደረውን ስሜት ለማወቅ ተጠባበቀ።
መምህራኑ ፈዘው ተመለከቱ፤ የሚያዩትን ማመን አቃታቸው።
አለቃ ግዕዛን፣ “ጥላዬ፣ ይኸ የፍቅር ውጤት ነው። ፍቅር ብቻ ነው ይኸን የመሰለ ሥራ ሊያሠራ ሚችለው። እስታሁን በሥራህ ደስተኛ ነበርሁ። ዛሬ ግን ይኸን የመሰለ የላቀ ሥራ ስላሳየኸኝ አከብርሃለሁ።
ይኸን የመሰለ የጥበብ ውጤት እንዳይ ዕድሜ ለሰጡኝ ሥላሤ ምስጋናዬን ሳቀርብ፣ ላንተ ደግሞ አድናቆቴን ገልጣለሁ። አንተም ሥላሤን ብቻ ሳይሆን እኔንም ነው ያከበርኸኝ። እኔን እንዳከበርኸኝ አንተን ደሞ ሥላሤ ያክብሩህ። አንተ የሥዕል ንጉሥ ነህ። ከይኸ ቀደም ማንም አልቀደመህም፣ አሁንም ሚደርስብህ የለም ወደፊትም ሚተካህ ዠግና
ሚመጣበት ግዝየ ሩቅ ነው” አሉት፣ ደብቀውና ተጠንቅቀው የያዙትን፣ለማንም ተማሪ አድረገውት የማያውቁትን ምስጋና እያዘነቡለት።
ጥላዬ እግዚሐር ይስጥልኝ ማለት ፈልጎ፣ ልሳኑ ተዘጋበት። በዝምታ
እግራቸው ሥር ተደፋ።
“ተነስ ልዥ ። ንጉሥ እሰው እግር ሥር ኣይወድቅም” አሉት።
ሊቀጠበብት አዳሙም፣ “ውነትም የሥዕል ንጉሥ ነህ። አንተ ዛሬ
ግዕዛንን ብቻ ሳይሆን ሁላችንንም ነው ያከበርኸው፣ ያኮራኸው። ውበት ማለት ይኸ እንጂ ሌላ ምን አለ? አንተ ለብዙ ተማሮች አርአያ
ትሆናለህ። ሚያሳዝነው ሥዕል እንደዝኸ ድንቅ ነገር ሁኖ ሳለ እንደ ቅኔና ዜማ በርካታ ተማሮች የሉትም። ደብረ ወርቅ እንደመጣህና ትምርት እኔጋ እንደዠመርህ፣ ውነትም የሥዕል ንጉሥ እንደምትሆን አውቄ ነበር። የናትህ ማጠን ይለምልም። ዛሬ የአለቃ ሔኖክ ነፍስም በሰማይ ቤት ትዘምራለች። ሥላሤ እጅህን ያለምልሙት” ብለው
ሊስሙት ሲጠጉት፣ ፈጠን ብሎ እግራቸውን ሳመ።
አለቃ ተክለየሱስና ሊቀጠበብት ያሬድም አድናቆትና ምስጋና
አዥጎድጎዱለት፤ ባረኩት፤ እንኳን ደስ ያለህ ብለው ሳሙት። እሱም
እግራቸውን ሳመ።
በምስክር ፊት በሥዕል ትምህርት ተመረቀ።
የመመረቂያውን አነስተኛ ድግስ እንዲቀምሱለት ሁሉንም ወደቤቱ
ይዟቸው ሄደ። እንጎች ያዘጋጀችውን ምግብ በልተው፣ አረቄ ጠጥተው አመስግነውትና መርቀውት ሊሄዱ ሲሉ፣ ሊቀጠበብት ያሬድ በድንገት
ሲቆሙ፣ ሌሎቹም ቆሙ።
ሁሉንም በተራ እየተመለከቱ፣ “በሉ ወንድሞቼ ኸመኼዳችን
በፊት አንድ ቅር ያለኝን ጉዳይ ልናገር ነው” አሉ። “ተማሪ እናታባቱ ያወጡለትን ስም እየተወ ለራሱ ስም ያወጣል። ዜማ ሲማር 'ጥዑመ ልሳን ነኝ ይላል። ቅኔ ሲማር ባሕረ ጥበብ ነኝ... ማንቴስ ነኝ ይላል።አንዳንዴም እሰበሱ ስም ይሸላለማል። ይኸ ልዣችን ግን ትሑትና የሥራ ሰው በመኾኑ ይኸው የባላገር ስሙን እንደያዘ ጥላዬ እንደተባለ
አለ። ምሥጢሩ ደግ ነው፤ ጥላ ከለላ ትኾነኛለኽ ሲሉ ማዶል አባቱ
“ጥላዬ ማለታቸው? ድንቅ ስም ነው። ግና ለእንዳንተ ያለ ጠቢብ
ዛሬ እናንተ ወንድሞቼ ኸፈቀዳችኹልኝ 'ሥሙር' ብዬዋለኹ። ደሞም አይኾንም። ሠዓሊ ተኹኖ ጥላዬ መባል ምሥጢሩ አይገጥምም። ስለዚኸ
ፊቱኑ የነበረ ወግ ነው። መምህራን ለጥበብ ልዦቻቸው ይስማማል
ያሉትን ስም ይሽልማሉ። እና ምን ትላላችኹ? ሥሙር አይዶለም
ጥላዬ?”
ሁለቱም መምህራን በአንድ ድምጽ በደስታ አደነቁት፣ “ቃለ ሕይወት ያሰማዎ ጌታዬ፤ ድንቅ ነው፤ ሥሙር ነው፤ ስሙም አሰያየሙም የተገባ ነው” ብለው አጸኑለት።”
መምህሮቹ በደስታ እያውካኩ ሲሄዱ ሸኝቷቸው እንደተመለሰ መደብ ላይ ጋደም አለ። የተዋጣለት ሥራ እንደሠራ አረጋገጠ። ሕልሙ ሁሉ
እውን ሆነ። ቋራ እያለ ወለቴን ንጉሥ ኸወሰዳት እኔ የሥዕል ንጉሥ ማልሆን? ያለውን አስታወሰ።ምኞቱ ሠመረ።
ዝናው በደብረ ወርቅ ብቻ ሳይሆን፣ አድባራቱን አልፎ መርጡለማርያም ድረስ ዘለቀ። በየደብሩ ያሉት የሥዕል መምህራን እንዲያስተምር
ገፋፉት። ዝናውን የሰሙ የአካባቢው ባላባቶች ደብራቸውን እንዲያስጌጥ ተረባረቡበት።
እሱ ግን አንዴ ለአንዱ ባላባት አድሮ መሥራት ከጀመረ ወደሌላው መሄድ ስለማይችል ለማንም አልታዘዝ አለ። በተጨማሪ፣ ሥዕል ታሪክ
ተናጋሪ፣ አስተማሪ፣ አብራሪ፣ ስሜትንና አእምሮን ቀስቃሽ እንጂ ለስም መጠሪያ ቤተክርስቲያን ማስዋቢያ ብቻ ሆኖ መወሰድ እንደሌለበት ተናገረ። በባላባቱ ዘንድ ቅሬታን አተረፈ።
ጐንደር ተመልሶ መሄድ ፈልጎ ከሀያ ዓመት በላይ በመቆየቱ
ባይተዋር የሚሆን መሰለው። ጐንደርን እንደዛ ወዶ ይህን ያህል
ርቆ መቀመጡ አልገባ አለው። ደብረ ወርቅ ብዙ አስተምራዋለች።
በርግጥም የሥዕል ንጉሥ አድርጋዋለች። ሆኖም ደብረ ወርቅ
የሕዝብ ዓይነት አይታይባትም። ደብረ ወርቅ ነዋሪዎቿን
የጐንደርን ዓይነት ታላቅነትና ግርማ ሞገስ የላትም። እንደ ጐንደር አድርጋ የመቀመጥ ባህርይ ሲኖራት፣ ጐንደር አደባባይ አውጥታ ታሟግታቸዋለች፤ የቤተክርስቲያን ምርጫ ትሰጣቸዋለች፣ ለድሆቿ
የእንፋሎት መታጠቢያ እንኳን አዘጋጅታለች።
ታዲያ ይህችን ጐንደርን እንዴት አድርጎ ለዘላለም ይተዋት? እንደ
ወለቴ የልጅነት ፍቅሩ፣ የጎልማሳ ዘመኑ ትዝታው አይደለችምን?
ጐንደር ለመሄድ ባሰበ ቁጥር፣ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር
ወዳጅነት ያዙ” የሚለውን ወሬ መርሳት ስላልቻለ ልቡ ያመነታል።
ባሏ ከሞቱ ጊዜ የቀድሞው ስሜቱ አንሰራርቶ የነበረው ዜናውን
ሲሰማ ልቡ ተሰርጉዶ ምንትዋብ ላይ ቅሬታ አድሮበታል።
በምንትዋብ ቅር መሰኘቱ ቅር የሚያሰኘው አልፎ አልፎ ደግሞ
የሚያስቀው ነገር ሆኖ አግኝቶታል ቅሬታው የመነጨው እኔ ይህን
ያህል ስለእሷ ሳስብ እሷ እንዴት ሳታስፈልገኝ ቀረች በሚል ነው።
የሚያስበው ሁሉ ተገቢ እንዳልሆነ ቢያውቅም፣ “ውነት ትወደኝ ኸነበረ እንዴት አታስፈልገኝም?” ብሎ ደግሞ በስጨት ይላል። በሌላ በኩል አፄ በካፋ ሲሞቱ ልቡ ውስጥ የተስፋ ጭላንጭል የተቀረፀበትን ጊዜ ያስብና ከት ብሎ ይስቃል። ድጋሚ ሌላ ሥዕል ሊልክላት ወሰነ።ሆኖም እንደመነኩሴው ታማኝ ሰው እንዴትና የት እንደሚያገኝ ማሰብ
አቃተው።
ቀደም ብሎ ስለአብርሃ ወሬ ይሰማ የነበረውን ያህል ባለመስማቱም በሕይወት ይኖር ይሆን እያለ መጨነቁም አልቀረም። ካንድ ሁለት
ጊዜ መልዕክት ልኮበት ሳይደርሰው ቀርቶ ይሁን ወይንም ደርሶት ዝም ብሎት እንደሆነ ለማወቅ ተቸገረ።
አንድ ቀን፣ ደብረ ወርቅ ማርያም ውስጥ የቅኔ መምህር ከሆኑት
ከመጋቤ ሥነ-ጊዮርጊስ ጋር ቤተክርስቲያኗ ግቢ ውስጥ ያለ ጥድ ስር ተቀምጠው ሲጨዋወቱ በቅርቡ ጐንደር ሄደው እንደነበር ነገሩት።
“እደብረብርሃን ሥላሤ ደርሰው ነበር?” አላቸው።
“አዎን።”
“እንዲያው መጋቤ አብርሃ ሚባል ጓደኛ ነበረኝ። መልክትም
ብልክበት አልደረሰው ሁኖ ነው መሰለኝ መልስም አልሰጠኝ።”
“አሉ። መቸም ጐንደር ኻፈራቻቸው ሊቃውንት አንዱ ናቸው ነው ሚሉ።”
ጥላዬ ደስ አለው። ጐንደር የመሄድ ፍላጎቱ ተነሳሳ።
“እንዴት ያለ ጥሩ ነገር ነገሩኝ። እኔማ ተጨንቄ ቆይቻ።”
👍10
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ደብረ ወርቅ ማርያም የሥዕል ንጉሥ አለ።”
የአስራ ስምንት ዓመቱ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በትምህርት የበሰለ፣
በአስተሳሰቡ የበለፀገ፣ በመልኩና በአቋሙ ያማረ ሆነላት ምንትዋብ።ፈረስ ላይ ተቀምጦ፣ ነጭ ሻሹን ሹሩባው ላይ አስሮ፣ በወርቅ ያጌጠ ካባውን ደርቦ፣ የወርቅ በትረ መንግሥቱን ጨብጦ፣ ቀይ ድባብ ተይዞለት፣ ባልደራስ አጅቦት ከግቢ ሲወጣ፣ ሕዝቡ፣ “አቤት አበቃቀሉ!
አቤት የፊቱ አወራረድ!” እያለ አደነቀው: ወደደው፤ አከበረው፤
ሰገደለት፤ “ቋረኛው ኢያሱ” የሚል ቅጽል ስምም አወጣለት።
አደን አፍቃሪው ኢያሱ እንደ በፊቱ ሰስና ድኩላን ሳይሆን፣ ዝሆን፣
አውራሪስና ጎሽ እየገደለ መምጣት ጀምረ። ምንትዋብና እናቷ ግን ለአደን በወጣ ቁጥር ወገባቸውን በገመድ እየታጠቁ፣ መሬት እየተኙ፣ እየጸሙና እንቅልፍ እያጡ ይሰነብታሉ።
ኢያሱ በድፍረቱና በጀግንነቱ ተወዳዳሪ አጣ። ስለሃገር ጉዳይም መከታተል፣ ውሳኔ መስጠትና እርምጃ መውሰድ ያዘ። ከእናቱ መዳፍ ሥር ወጥቶ የራሱ ሰው ሆነ። አክሱም ጽዮን ሄደ። የእናቱን የትውልድ
ቦታ ለማየትም ቋራ ደርሶ መጣ። አንድ ጊዜ የግዛት ማስፋፋት ፍላጎቱ አድጎ ሰቆጣ ሄዶ ተሸንፎ ቢመጣ፣ በቁጭት ወኔውን ሞልቶ ሱዳን ጠረፍ ሄደ፡፡
የገጠመውን ጦር አሸንፎ በሰላም ተመለሰ።
በሰላም ይመለስ እንጂ ከእናቱ ጋር አተካራና ቅያሜ ውስጥ ገባ።
በግራዝማች ኢያሱና በእናቱ መሃል ያለው የፍቅር ግንኙነት ይከነክነው
ገባ። ምንትዋብም ወለተእስራኤል ያለቻትን ሦስተኛ ልጇን ከወለደች
ቆይታለች።
ኢያሱ እናቱ ላይ ቅሬታና ምሬት አደረበት። ምንም እንኳ እናቱን
ቢያከብርና ቢፈራ፣ ከግራዝማች ኢያሱ ጋር ያላትን ግንኙነት ችላ
የማይለው ጉዳይ ሆነበት።
ፀሐይ መግቢያ ላይ ነው። እናትና ልጅ ቤተመንግሥት እንግዳ
መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ኢያሱ ነገር ሲገባው ታውቃለች
ምንትዋብ። ገና፣ “ኸያሱ ጋር..” ሲልና ሲጠጣበት የነበረውን የወርቅ ዋንጫ ሲያስቀምጥ፣ የንግግራቸው አቅጣጫ ወዴት እንደሆነ ገባት።
“ኸያሱ ጋር ባለሽ ግንኙነት ሰው ሁሉ ያማሻል። ቀደም ብየ ብሰማም ዕድሜየም ገና ስለነበር ፈርቸ እስተዛሬ በዝምታ ቆየሁ” አላት።
“ኢያሱ አባትህኮ ሲሞቱ ዕድሜዬ ገና ነበር። ብቸኛም ነበርሁ።
ልችም መውለድ ፈልግ ነበር። ደሞስ እንዲህ ያለው በኔ ተዠመረ?” አለችና፣ ለራሷ ዛዲያ እንዴት ልሁን ሰው መሆኔ ቀረ? እቴጌ ያሉኝ እንደሁ ሰው ማይደለሁ እንዴ? ሰው መሆን ዛዲያ ትርጉሙ ምኑ ላይ ነው? ስትል መናገር ሲጀምር ቀና አለች።
“የመዠመርና ያለመዠመር ጉዳይ ማዶል” አለ፣ እናቱ ላይ አድርጎ
በማያውቀው መንገድ ፊቱን አኮማትሮ።
ከእሷ ስሜት በላይ ክብር የሚባል ነገር አለ።
መልስ አልሰጠችውም። ስሜቱ እንደተጎዳ አውቃለች። እባክህ
አምላኬ ኸልዤ ጋር እንዳልጣላ ትግስት ስጠኝ አለች።
“ኢያሱ አንደኛ ያክስቴ ልዥ ነው” ሲል ቀጠለ። “ያባቴ እት...
የወለተስራኤል ልዥ እኮ ነው። ያባቴ ክብርስ ቢሆን፣ ስለምን ይነካል? ላንቺም ቢሆን ነውር ነው። ስለምንስ ስማችን በዝኸ ይነሳል? መልካም ስምሽንስ ስለምን ታጎድፊያለሽ? ግራማች ብትይውም ሰዉ አሁንም
ምልምል ኢያሱ ነው ሚለው። ኸዝኸ ወዲያ ውርደት ምን አለ?”
ንግግሩ ጎመዘዛት። ከንፈሯን በጥርሷ ነከስ ኣድርጋ በግራ ሌባ ጣቷ መታ መታ አደረገችው። ቁጣ ሰውነቷ ውስጥ ሲቀሰቀስ ተሰማት።
“ተው እንጂ ኢያሱ! እኔን እናትህን እንዲህ አትናገር። ምወድህ
እናትህ እንጂ ሌላ ነኝ?”
“ሰዉ ያማሻል እኮ!” ግንባሩ ኩምትር ብሏል።
“አምተው በቅቷቸዋል። ኢያሱ ... ኸግራማች ጋር ተዋልደናል እኮ!
እህቶችህ የማን ይመስሉሃል? እኔ ያባትህን ስም ለማጉደፍ ሳይሆን፣
ብቸኝነት ስላጠቃኝ ነው። ተረዳኝ እንጂ!”
“ኸዝኽ ወዲያ ውርደት ምን አለ?” የሚሉት ቃላቶቹ ረበሿት። ትክ ብላ አየችው። ፊቱ ላይ ቅያሜ አየች። ዛዲያ ዕድሜዬን እንዲሁ
ላሳልፍ ኑሯል እንዴ? አለች።
ለእሱ የክብር ጉዳይ እንደሆነ አላጣችውም። እንኳንስ የባሏን
የእህት ልጅ ባሏ የሞተባት ንግሥት ጨርሶ ሌላ ማግባት እንደሌለባት ታውቃለች።
ግን ደግሞ ውጣ ውረድ ከበዛበት የቤተመንግሥት ሕይወት ዘወር ብላ የምትዝናናበትና ሐሳቧን የምትከፍልበት ነገር ባለመኖሩ፣
አንድ ቀን ከልጇ ጋር የሚያቃቅራትና አልፎም ሊያጣላት የሚችል ነገር እንደሆነ ብታውቅም አድርጋዋለች።
ከልጇ ጋር ይህን ያህል ጠንከር ያለ ንግግር ተለዋውጠው ስለማያውቁ ቅር ብትሰኝም፣ የምትወደውንና የምትሳሳለትን ገራሙን ልጇን መቀየም
አልሆነላትም። ቅሬታና ቅይሜ በሆዷ አምቃ መሄድ አልፈለገችም።
የአባቱ ብቻ ሳይሆን የእሱ፣ ብሎም የእሷ ክብር እንደተነካበት ስላወቀች ትችቱን ተቀብላ ዋጥ ማድረግን ፈለገች።
በራሷ አምሳል ቀርጻ ያወጣችው ቢመስላትም፣ እየተመካከረች፣
ሲሻትም እየተጫነችው ያሳደገችው ልጇ ብሩህ አእምሮ ያለውና በራሱ አስተሳሰብ የሚመራ መሆኑን በመገንዘብ ልቧ ላይ ሊሰርፅ የቃጣውን
ቅሬታ ለመግታት ታገለች።
ለብቻው ለመግዛት ዕድሜው ቢፈቅድለትም፣ ለእሷ ካለው ፍቅር፣አክብሮትና ፍራቻ ጭምር የእሷን የበላይነት ተቀብሎ መኖር እንደቻለ ተገነዘበች። እሱም ቢሆን ከሥልጣኗ ለማውረድ የሚያስችለው በቂ
ምክንያት የለውም።
እንዲያውም የእሱ መንግሥት በእሷ ብርታት፣ ጥበብና ዘዴ የተሞላው አመራር መደላደሉን፣ አንዳንድ መኳንንት ቋረኞች ላይ ያላቸውን ጥላቻ አርግባ ተስማምታና አስማምታ መቆየቷን፣ ከአንዴም ሁለት
ጊዜ የተቃጣባቸውን ዓመጽ ድል መቀዳጀታቸውን፣ ሌሎችን ደግሞ
በሰላማዊ ድርድር እየፈታች ሰላም እንዲሰፍን ማድረጓን ይገነዘብ
እንደሆነ ራሷን ጠየቀች። ይህን ልታስታውሰው ግን አልፈለገችም፤
ዝም ብላ ተቀመጠች። ተነስቶ ሲወጣ በተለመደው የእናትና የልጅ ፍቅር አልተሰነባበቱም።
ከሄደ በኋላ፣ የተነጋገሩትን ሁሉ በጭንቅላቷ ከለሰችው። መቸም
እኔስ ብሆን በነገሩ ሳልጨነቅ ቀርቸ ነው? አልሆንልኝ ብሎ ነው እንጂ።ብቸኝነት አጥቅቶኝ ነው ኸኢያሱ ጋር እዚህ ሁሉ ውስጥ የገባሁት።እሱም ቢሆን እነአስቴርን የመሳሰሉ ልዦች ሰጥቶኛል። ኸንግዲህ
ምን አረጋለሁ። የአብራኬ ክፋይ እንዲህ ሲለኝ መስማት ለእኔ ደግ
ማዶል። መቸስ የክብር ጉዳይ ሆኖበት ነው። በዝኸ አልቀየመውም። እነሱ እንዳይጣሉብኝ እንጂ። ለግራማች ኢያሱ ነግረዋለሁ እያለች አሰላሰለች።
ግራዝማች ኢያሱ፡ “ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ተለውጦብኛል” ማለት
ሲያዘወትር፣ እንዳይጣሉባት ሰጋች፤ በሐሳብ ባከነች። እየቆየም በሁለቱ መሃል ነገሮች እየከረሩ፣ ግንኙነታቸው ወደ ፀብ መቀየሩ እንቅልፍ አሳጣት። አስታራቂ ሽማግሌዎች ላከች።
ይህ ሳያንሳት በመጋቤ ሥነ-ጊዮርጊስ አማካኝነት ሁለተኛው የጥላዬ ሥዕል መጣላት። የሥዕሉ ውበትና የያዘው ጥልቅ ሐሳብ
ቢያስደስታትም፣ ሁለቱም ሥዕሎች ከአንድ ሥሙር ከሚባል ሰው መምጣታቸውን በሥራው አረጋገጠች፤ ለወራት ተረበሸች።
እነዚህን ሥዕሎች የሚልከው ሰው ምን አስቦ እንደሆነ ለማወቅ
ቸገራት። እኼ ሰው ስለምን ማንነታቸው ስንኳ በማይታወቅ ሰዎች ይልካል? ይኸ ከበጎ አሳብ የመጣ ነው ወይንስ እኔን ሰላም ለመንሳት ሚደረግ እኔ ለራሴ ኸልዤ ጋር ችግር ውስጥ በገባሁበት ግዝየ ስለምን
እንደዝኸ ያለ ነገር ይገጥመኛል? አንቺ ምወድሽ ቁስቋም የዝኸን ሰው ማንነት አንቺው ግለጭልኝ እያለች ማርያምን ተለማመነች። ለሌላ ሰው የማታዋየው ምሥጢር ሆኖባት ሥዕሉን በመጣበት ጨርቅ መልሳ ጠቅልላ ከበፊተኛው ሥዕል ጋር ደብቃ አስቀመጠችው።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ደብረ ወርቅ ማርያም የሥዕል ንጉሥ አለ።”
የአስራ ስምንት ዓመቱ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በትምህርት የበሰለ፣
በአስተሳሰቡ የበለፀገ፣ በመልኩና በአቋሙ ያማረ ሆነላት ምንትዋብ።ፈረስ ላይ ተቀምጦ፣ ነጭ ሻሹን ሹሩባው ላይ አስሮ፣ በወርቅ ያጌጠ ካባውን ደርቦ፣ የወርቅ በትረ መንግሥቱን ጨብጦ፣ ቀይ ድባብ ተይዞለት፣ ባልደራስ አጅቦት ከግቢ ሲወጣ፣ ሕዝቡ፣ “አቤት አበቃቀሉ!
አቤት የፊቱ አወራረድ!” እያለ አደነቀው: ወደደው፤ አከበረው፤
ሰገደለት፤ “ቋረኛው ኢያሱ” የሚል ቅጽል ስምም አወጣለት።
አደን አፍቃሪው ኢያሱ እንደ በፊቱ ሰስና ድኩላን ሳይሆን፣ ዝሆን፣
አውራሪስና ጎሽ እየገደለ መምጣት ጀምረ። ምንትዋብና እናቷ ግን ለአደን በወጣ ቁጥር ወገባቸውን በገመድ እየታጠቁ፣ መሬት እየተኙ፣ እየጸሙና እንቅልፍ እያጡ ይሰነብታሉ።
ኢያሱ በድፍረቱና በጀግንነቱ ተወዳዳሪ አጣ። ስለሃገር ጉዳይም መከታተል፣ ውሳኔ መስጠትና እርምጃ መውሰድ ያዘ። ከእናቱ መዳፍ ሥር ወጥቶ የራሱ ሰው ሆነ። አክሱም ጽዮን ሄደ። የእናቱን የትውልድ
ቦታ ለማየትም ቋራ ደርሶ መጣ። አንድ ጊዜ የግዛት ማስፋፋት ፍላጎቱ አድጎ ሰቆጣ ሄዶ ተሸንፎ ቢመጣ፣ በቁጭት ወኔውን ሞልቶ ሱዳን ጠረፍ ሄደ፡፡
የገጠመውን ጦር አሸንፎ በሰላም ተመለሰ።
በሰላም ይመለስ እንጂ ከእናቱ ጋር አተካራና ቅያሜ ውስጥ ገባ።
በግራዝማች ኢያሱና በእናቱ መሃል ያለው የፍቅር ግንኙነት ይከነክነው
ገባ። ምንትዋብም ወለተእስራኤል ያለቻትን ሦስተኛ ልጇን ከወለደች
ቆይታለች።
ኢያሱ እናቱ ላይ ቅሬታና ምሬት አደረበት። ምንም እንኳ እናቱን
ቢያከብርና ቢፈራ፣ ከግራዝማች ኢያሱ ጋር ያላትን ግንኙነት ችላ
የማይለው ጉዳይ ሆነበት።
ፀሐይ መግቢያ ላይ ነው። እናትና ልጅ ቤተመንግሥት እንግዳ
መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ኢያሱ ነገር ሲገባው ታውቃለች
ምንትዋብ። ገና፣ “ኸያሱ ጋር..” ሲልና ሲጠጣበት የነበረውን የወርቅ ዋንጫ ሲያስቀምጥ፣ የንግግራቸው አቅጣጫ ወዴት እንደሆነ ገባት።
“ኸያሱ ጋር ባለሽ ግንኙነት ሰው ሁሉ ያማሻል። ቀደም ብየ ብሰማም ዕድሜየም ገና ስለነበር ፈርቸ እስተዛሬ በዝምታ ቆየሁ” አላት።
“ኢያሱ አባትህኮ ሲሞቱ ዕድሜዬ ገና ነበር። ብቸኛም ነበርሁ።
ልችም መውለድ ፈልግ ነበር። ደሞስ እንዲህ ያለው በኔ ተዠመረ?” አለችና፣ ለራሷ ዛዲያ እንዴት ልሁን ሰው መሆኔ ቀረ? እቴጌ ያሉኝ እንደሁ ሰው ማይደለሁ እንዴ? ሰው መሆን ዛዲያ ትርጉሙ ምኑ ላይ ነው? ስትል መናገር ሲጀምር ቀና አለች።
“የመዠመርና ያለመዠመር ጉዳይ ማዶል” አለ፣ እናቱ ላይ አድርጎ
በማያውቀው መንገድ ፊቱን አኮማትሮ።
ከእሷ ስሜት በላይ ክብር የሚባል ነገር አለ።
መልስ አልሰጠችውም። ስሜቱ እንደተጎዳ አውቃለች። እባክህ
አምላኬ ኸልዤ ጋር እንዳልጣላ ትግስት ስጠኝ አለች።
“ኢያሱ አንደኛ ያክስቴ ልዥ ነው” ሲል ቀጠለ። “ያባቴ እት...
የወለተስራኤል ልዥ እኮ ነው። ያባቴ ክብርስ ቢሆን፣ ስለምን ይነካል? ላንቺም ቢሆን ነውር ነው። ስለምንስ ስማችን በዝኸ ይነሳል? መልካም ስምሽንስ ስለምን ታጎድፊያለሽ? ግራማች ብትይውም ሰዉ አሁንም
ምልምል ኢያሱ ነው ሚለው። ኸዝኸ ወዲያ ውርደት ምን አለ?”
ንግግሩ ጎመዘዛት። ከንፈሯን በጥርሷ ነከስ ኣድርጋ በግራ ሌባ ጣቷ መታ መታ አደረገችው። ቁጣ ሰውነቷ ውስጥ ሲቀሰቀስ ተሰማት።
“ተው እንጂ ኢያሱ! እኔን እናትህን እንዲህ አትናገር። ምወድህ
እናትህ እንጂ ሌላ ነኝ?”
“ሰዉ ያማሻል እኮ!” ግንባሩ ኩምትር ብሏል።
“አምተው በቅቷቸዋል። ኢያሱ ... ኸግራማች ጋር ተዋልደናል እኮ!
እህቶችህ የማን ይመስሉሃል? እኔ ያባትህን ስም ለማጉደፍ ሳይሆን፣
ብቸኝነት ስላጠቃኝ ነው። ተረዳኝ እንጂ!”
“ኸዝኽ ወዲያ ውርደት ምን አለ?” የሚሉት ቃላቶቹ ረበሿት። ትክ ብላ አየችው። ፊቱ ላይ ቅያሜ አየች። ዛዲያ ዕድሜዬን እንዲሁ
ላሳልፍ ኑሯል እንዴ? አለች።
ለእሱ የክብር ጉዳይ እንደሆነ አላጣችውም። እንኳንስ የባሏን
የእህት ልጅ ባሏ የሞተባት ንግሥት ጨርሶ ሌላ ማግባት እንደሌለባት ታውቃለች።
ግን ደግሞ ውጣ ውረድ ከበዛበት የቤተመንግሥት ሕይወት ዘወር ብላ የምትዝናናበትና ሐሳቧን የምትከፍልበት ነገር ባለመኖሩ፣
አንድ ቀን ከልጇ ጋር የሚያቃቅራትና አልፎም ሊያጣላት የሚችል ነገር እንደሆነ ብታውቅም አድርጋዋለች።
ከልጇ ጋር ይህን ያህል ጠንከር ያለ ንግግር ተለዋውጠው ስለማያውቁ ቅር ብትሰኝም፣ የምትወደውንና የምትሳሳለትን ገራሙን ልጇን መቀየም
አልሆነላትም። ቅሬታና ቅይሜ በሆዷ አምቃ መሄድ አልፈለገችም።
የአባቱ ብቻ ሳይሆን የእሱ፣ ብሎም የእሷ ክብር እንደተነካበት ስላወቀች ትችቱን ተቀብላ ዋጥ ማድረግን ፈለገች።
በራሷ አምሳል ቀርጻ ያወጣችው ቢመስላትም፣ እየተመካከረች፣
ሲሻትም እየተጫነችው ያሳደገችው ልጇ ብሩህ አእምሮ ያለውና በራሱ አስተሳሰብ የሚመራ መሆኑን በመገንዘብ ልቧ ላይ ሊሰርፅ የቃጣውን
ቅሬታ ለመግታት ታገለች።
ለብቻው ለመግዛት ዕድሜው ቢፈቅድለትም፣ ለእሷ ካለው ፍቅር፣አክብሮትና ፍራቻ ጭምር የእሷን የበላይነት ተቀብሎ መኖር እንደቻለ ተገነዘበች። እሱም ቢሆን ከሥልጣኗ ለማውረድ የሚያስችለው በቂ
ምክንያት የለውም።
እንዲያውም የእሱ መንግሥት በእሷ ብርታት፣ ጥበብና ዘዴ የተሞላው አመራር መደላደሉን፣ አንዳንድ መኳንንት ቋረኞች ላይ ያላቸውን ጥላቻ አርግባ ተስማምታና አስማምታ መቆየቷን፣ ከአንዴም ሁለት
ጊዜ የተቃጣባቸውን ዓመጽ ድል መቀዳጀታቸውን፣ ሌሎችን ደግሞ
በሰላማዊ ድርድር እየፈታች ሰላም እንዲሰፍን ማድረጓን ይገነዘብ
እንደሆነ ራሷን ጠየቀች። ይህን ልታስታውሰው ግን አልፈለገችም፤
ዝም ብላ ተቀመጠች። ተነስቶ ሲወጣ በተለመደው የእናትና የልጅ ፍቅር አልተሰነባበቱም።
ከሄደ በኋላ፣ የተነጋገሩትን ሁሉ በጭንቅላቷ ከለሰችው። መቸም
እኔስ ብሆን በነገሩ ሳልጨነቅ ቀርቸ ነው? አልሆንልኝ ብሎ ነው እንጂ።ብቸኝነት አጥቅቶኝ ነው ኸኢያሱ ጋር እዚህ ሁሉ ውስጥ የገባሁት።እሱም ቢሆን እነአስቴርን የመሳሰሉ ልዦች ሰጥቶኛል። ኸንግዲህ
ምን አረጋለሁ። የአብራኬ ክፋይ እንዲህ ሲለኝ መስማት ለእኔ ደግ
ማዶል። መቸስ የክብር ጉዳይ ሆኖበት ነው። በዝኸ አልቀየመውም። እነሱ እንዳይጣሉብኝ እንጂ። ለግራማች ኢያሱ ነግረዋለሁ እያለች አሰላሰለች።
ግራዝማች ኢያሱ፡ “ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ተለውጦብኛል” ማለት
ሲያዘወትር፣ እንዳይጣሉባት ሰጋች፤ በሐሳብ ባከነች። እየቆየም በሁለቱ መሃል ነገሮች እየከረሩ፣ ግንኙነታቸው ወደ ፀብ መቀየሩ እንቅልፍ አሳጣት። አስታራቂ ሽማግሌዎች ላከች።
ይህ ሳያንሳት በመጋቤ ሥነ-ጊዮርጊስ አማካኝነት ሁለተኛው የጥላዬ ሥዕል መጣላት። የሥዕሉ ውበትና የያዘው ጥልቅ ሐሳብ
ቢያስደስታትም፣ ሁለቱም ሥዕሎች ከአንድ ሥሙር ከሚባል ሰው መምጣታቸውን በሥራው አረጋገጠች፤ ለወራት ተረበሸች።
እነዚህን ሥዕሎች የሚልከው ሰው ምን አስቦ እንደሆነ ለማወቅ
ቸገራት። እኼ ሰው ስለምን ማንነታቸው ስንኳ በማይታወቅ ሰዎች ይልካል? ይኸ ከበጎ አሳብ የመጣ ነው ወይንስ እኔን ሰላም ለመንሳት ሚደረግ እኔ ለራሴ ኸልዤ ጋር ችግር ውስጥ በገባሁበት ግዝየ ስለምን
እንደዝኸ ያለ ነገር ይገጥመኛል? አንቺ ምወድሽ ቁስቋም የዝኸን ሰው ማንነት አንቺው ግለጭልኝ እያለች ማርያምን ተለማመነች። ለሌላ ሰው የማታዋየው ምሥጢር ሆኖባት ሥዕሉን በመጣበት ጨርቅ መልሳ ጠቅልላ ከበፊተኛው ሥዕል ጋር ደብቃ አስቀመጠችው።
👍14
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....የቁስቋም ግቢ ግብር አዳራሽም ሥራ በተቀላጠፈ መንገድ ተያያዘ።አዳራሹ ውስጡ ከላይም ከታችም ለምንትዋብና ለኢያሱ መቀመጫ የሚሆን ገባ ያለ ቦታ ተሠራለት። በስተቀኝ በኩል ስድስት፣ በስተግራ
ደግሞ አምስት ማሾ ማስቀመጪያ ሸክላዎች የሚይዙ ድፍን መስኮቶች ተደረጉለት።
ሠራተኛው ከፊሉ ድንጋይ ሲያግዝ፣ ሌላው ዕንጨት ሲያቀርብ፣የቀረው ሲለስን፣ ኖራ ሲቀባ፣ አነዋሪው ተቀምጦ ወይም ቆሞ እየተዟዟረ ሲያነውር፣ የተበላሸውን ሲጠቁም፣ በትክክል ያልተለሰነ ወይንም በትክክል ያልገባ ዕንጨት ወይንም ድንጋይ ሲያይ ሲጠቁም ኢያሱ
ከሠራተኛ ጋር ሲሠራ፣ እናትና ልጅ እርስ በእርስ፣ ከሙያተኞችና
ከሠራተኞች ጋር ሲወያዩ፣ ሐሳብ ሲሰሙና ሲሰጡ ይቆያሉ።
“እስቲ በሉ የተበላሸ ያያችሁትን ተናገሩ” ትላቸዋለች ምንትዋብ፣
ሠራተኞቹን።
“እቴጌ ኸግማርዳ ጥዱ አይሻልም ኑሯል?” ይላታል አንዱ ግንበኛ።
“ግማርዳ ነው እንጂ ለንድህ ያለው” ይላል ሌላው።
“ሁሉም ለመጡበት ጉዳይ ያገልግላሉ” ይላሉ እናትና ልጅ።
ሠራተኞቹ ነገሥታቱ ከእነሱ ጎን ሆነው መሥራታቸው፣ የእነሱን ሐሳብ መስማታቸው አስደነቃቸው። እንደ ሰማይ ከዋክብት ሩቅ የመሰሏቸው፣ ብሎም እንደነሱ ከስጋና ከደም የተሰሩ የማይመስሏቸው የነበሩት ነገሥታት ሰው ሆነው አገኟቸው። በተለይም ደግሞ ኢያሱ ራሱ ሥራው ላይ ተሰማርቶ ከእነሱ እኩል ሲቀባና ሲሠራ አይተው
ተደመሙ።
ወትሮውንም ማንም ፍርድ ፈላጊ ሰተት ብሎ ቤተመንግሥት ገብቶ
እንዲዳኝ ስላደረገ፣ ፍትሕ ለጎደለበት ፍትሕ ስለሰጠና ለድኃ ስለቸረ ይወዱትና ይሳሱለት ነበረና እንደዚህ በቅርብ ከነሱ ጋር ሲሠራ ሲያዩት ይበልጥ ወደዱት።
አንድ ጠዋት ሠራተኞቹ በግብር አዳራሹ አንድ ወገን ላይ እየተሠራ
ስላለው ረጅም የእንቁላል ቅርጽ ያለው ግንብ ድምጻቸውን ዝቅ
አድርገው ያወራሉ። ምንትዋብና ኢያሱ ጎን ለጎን ቆመው የተሠራውን ሥራ ይመለከታሉ።
“አላየህም እንዴ ኸዛ ላይ ሁነህ? ቀሀ እኮ ወለል ብሎ ይታያል” አለ፣
አንዱ ግንበኛ።
“ቀሀ ትላለህ? ጣና ይታይ የለ? ቀሀማ ኸዝሁ ነው።” ከት ብሎ ሳቀ ሌላው።
“ጣና ይታያል ነው ምትሉት?” አለች ምንትዋብ፣ በመገረም።
“አዎ እቴጌ ሲያልቅ ያዩታል። እንዲያው ጣና ወለል ብሎ ነው
ሚታይ” ኣላት፣ አንደኛው ግንበኛ።
“እስቲያልቅ ምን አቆየን፣ አሁን አናየውም?” አላት ኢያሱ።
እናትና ልጅ ፎቁ ላይ ወጡ።
“ውነት ነው ኢያሱ። ያውልህ ... ያ ሚታየው ጣና እኮ ነው። ይኸማ
ለጥበቃ አይሆንም። ለኔ ነው ሚሆን” አለችው።
“ውነትም ወለል ብሎ ይታያል። ቀሀም ይኸው። ውነትሽ ነው።
ላንቺ ይሆናል። ዐጥሩ ተሠርቶ ሲያልቅ ቁስቋም ፊት ለፊት እንደ
ተደረገው የጥበቃ ሰቀላዎቹ ዙርያውን ይሠራሉ።”
ምንትዋብ ደስ አላት። እንዴት እሰተ ዛሬ አላሰብሁትም ብላ
ተገረመች። የተመረጡ እንደ ግራዝማች ኢያሱ፣ ሮብዓምና ሌሎችም እንግዶች መቀበያና ለራሷም መዝናኛ እንደምታደርገው ወሰነች።
አንድ ቀን፣ ምንትዋብ አፄ ፋሲለደስ ቤተመንግሥት ልጇ ኢያሱጋ ለመሄድ፣ በልዩ ልዩ ጌጣ ጌጥ የተሸለመችው በቅሎዋ ላይ ተቀምጣ፣የእሷና የኢያሱ መግቢያና መውጫ ብቻ በሆነው በር ከዐጀቧ ጋር እንደ ሁልጊዜው ባለ ወርቀ ዘቦ ድባብ ተይዞላት ከግቢ ወጣች።
ቤተመንግሥት ስትገባ እንደወትሮው ሁሉም ሰገዱላት። ወደ ኢያሱ መኖሪያ አመራች። ኢያሱ ወጥቶ በደስታ ተቀበላትና ውስጥ ገብተው ጨዋታ ጀመሩ። ኢያሱ ልትነግረው የምትፈልገው ነገር ሲኖር ያውቃል። ምን ልትነግረው፣ ወይንም ምን ልትጠይቀው እንደፈለገች
በጉጉት መጠበቅ ለምዷል።
“ኢያሱ ዛሬ የመጣሁት” አለችው፣ በመጨረሻ። “አንድም አንተን
ለማየት ሌላም ቀደም ብሎ እንደተነጋገርነው ቃሮዳና ዙርያውን
የተተከለው ወይን እንዴት እንዳፈራ ልነግርህ ነው። ትናንት ይዘው
መጡ፤ መቸስ ጉድ ትላለህ። እንዳው ማማሩን ብታይ ጉድ ትላለህ።”
“እንዴት እንደዝኸ ተሎ ደረሰ?”
“ደረሰ። ይገርምሀል። እና አሁን የግብር ቤቱም ሥራ እያለቀ ነው።
ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ግብሩን በሰፊው እናርግላቸው።የስተዛሬው እንዳው በቂ ከልነበረም።”
“እናርግላቸው እንጂ አሁንማ። ምን እንጠብቃለን?”
“ወይኑ መጠመቅ እንዲጀምር ትዛዝ ሰጥቻለሁ።”
“መልካም ነው።”
ጥቂት ስለቤተመንግሥት ጉዳይ ከተወያዩ በኋላ ተነስታ ወጣች።
ከወራት በኋላ፣ አንድ ቅዳሜ ዳግማዊ ኢያሱ ማለዳ ላይ ቁስቋም መጣ።ሰማዩ ጥርት ብሏል። ፀሐይዋ ደምቃለች። ምንትዋብ ከቤተመንግሥቷ
በደረጃ ወጥታ ተቀበለችው። እያወሩ ቁልቁል ሲወርዱ ተሰርቶ
ያለቀውን የግብር አዳራሽ አይታ ንግግሯን አቋርጣ፣ “ኢያሱ እይልኝ!ጉድ በልልኝ! እይልኝ እንዴት እንደሚያምር!” አለችው። በደስታ እንደ ልጅ በጨፈረች ደስ ባላት፣ የቤተመንግሥት ሥርዐትና ዕድሜ አልፈቅድ ብለዋት እንጂ።
“ውነትሽ ነው ያምራል! ሁለዜ ስለምናየው እስታሁን እንደዝኸ
እንደዛሬው ማማሩን አላወቅነም እኮ።”
ምንትዋብ ቀልቧ ግንቡ ላይ ነው። አልሰማችውም።
በተጠጋች ቁጥር የግንቡ ግርማ ሞገስ አስደነቃት። የአሠራሩ ጥራት፣የልስኑ ማማርና መርቀቅ፣ የቀለሙ ውበት ከገመተችው በላይ ሆነባት።
ኣጠገቡ ሲቆሙ ስሜቷ አሽነፋትና እንባዋ ዱብ ዱብ አለ።
ከኋላቸው የቆሙት የቤተመንግሥት ባለሟሎች፣ ሠዓሊዎች፣ሮብዓም፣ ካህናትና ሊቃውንት አዳራሹን በአድናቆት ተመለከቱ።
ሁሉም በአንድ ላይ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “እዝጊሃር ያክብራችሁ።
የናንተ ሥራ ነው” እያሉ አመሰገኗቸው።ምንትዋብ መናገር ተስኗት የለም የለም የሁሉም ነው። ሰው ተረባርቦ ነው ይኸን መሳይ ታላቅ ሥራ የሠራው። ሁሉም ይመሰገናል። የሠሩትን
ሁሉ ትናንትም አመስግኛቸዋለሁ። ያለኝን ሁሉ ሰጥቻለሁ። እዝጊሃር
ያክብራቸው አለች፣ ለራሷ። ራሴን ማመስገን አይሁንብኝና ልክ
እንዳልሁት፣ ልክ በሰጠሁት አሳብ መሠረት እኮ ነው የተሠራ አለች።
ባልስን፣ በቀለም ምርጫና በአጠቃላይ ላይ አሻራዋን የጣለችበትን ግንብ እያየች።
በስተቀኝ በኩል ወደ ላይ የወጣውን እንቁላል ግንብ አይታ፣ እሱስ ቢሆን እንዴት አምራል? ኸ'ያሱ ጋር እንደልብ ቁጭ ብሎ ለማውራት ይመቻል አለች፣ በአደባባይ እንደልብ መገናኘት ሰለማይችሉት ስለ
ግራዝማች ኢያሱ አስባ። ኸመላከ ጠሐይ ሮብዓምም ጋር ጥሩ ወግ
መያዝ እችላለሁ ኸዝያ አለች።
ፊቷን ወደ ልጇ መልሳ፣ “ኢያሱ ኸላይ እግንቡ ላይ በግራ በኩል
ያሉትን የመስቀል ቅርጦች አየኻቸው? ቀጥሎ ያለውንስ ዘውድ?”
“ሁሉም ቁልጭ ብለው ይታያሉ። አየሽው ከጎኑ ያለውን በጉን
ሲገድል ሚታየው አንበሳ? ኸጎኑ አንበሳ ላይ የተቀመጠውስ ንጉሥ ያገራችን ምልክት! እንዴት ጥሩ ወጥቷል። ቀጥሎ ያሉት ዝሆንና
አንበሳስ እንዴት እንዳማሩ አየሽ?”
“አዎ ልክ አንተ እንዳልኸው ነው የተሠሩት። የጣድቁ የአባ
ሳሙኤልና የአቡነ ዮሐንስ ምስሎችስ ቢሆኑ እንዴት እንዳማሩ” አለች፣
የዋልድባውን መነኩሴ የአባ ሳሙኤልንና የዐዲሱን አቡን የዮሐንስን ምስል እየተመለከተች።
ራሷን አረጋግታ ዙርያውን ቃኘች። አስቀድማ ያሰበችው ሐሳብ
ሥራ ላይ የሚውልበት ሰዐት
ተቃርቧል።ወደ ኢያሱ ዞረች።
“ኢያሱ ኸዝኸ ኻዳራሹ በስተግራ በኩል ኻሰብሁት በላይ በቂ መሬትአለ። የሴቶች ሙያ ተማሪ ቤት ማሳነጽ ፈልጋለሁ ብዬ ማልነበር? ያውልህ ኸጠሎት ቤቱ ዠርባ ዋርካው አጠገብ ደሞ ሌላ ሰፊ መሬት።እሱም ቢሆን እንዳሰብሁት...”
“ምን አስበሽለት ነበር ለቦታው?”
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....የቁስቋም ግቢ ግብር አዳራሽም ሥራ በተቀላጠፈ መንገድ ተያያዘ።አዳራሹ ውስጡ ከላይም ከታችም ለምንትዋብና ለኢያሱ መቀመጫ የሚሆን ገባ ያለ ቦታ ተሠራለት። በስተቀኝ በኩል ስድስት፣ በስተግራ
ደግሞ አምስት ማሾ ማስቀመጪያ ሸክላዎች የሚይዙ ድፍን መስኮቶች ተደረጉለት።
ሠራተኛው ከፊሉ ድንጋይ ሲያግዝ፣ ሌላው ዕንጨት ሲያቀርብ፣የቀረው ሲለስን፣ ኖራ ሲቀባ፣ አነዋሪው ተቀምጦ ወይም ቆሞ እየተዟዟረ ሲያነውር፣ የተበላሸውን ሲጠቁም፣ በትክክል ያልተለሰነ ወይንም በትክክል ያልገባ ዕንጨት ወይንም ድንጋይ ሲያይ ሲጠቁም ኢያሱ
ከሠራተኛ ጋር ሲሠራ፣ እናትና ልጅ እርስ በእርስ፣ ከሙያተኞችና
ከሠራተኞች ጋር ሲወያዩ፣ ሐሳብ ሲሰሙና ሲሰጡ ይቆያሉ።
“እስቲ በሉ የተበላሸ ያያችሁትን ተናገሩ” ትላቸዋለች ምንትዋብ፣
ሠራተኞቹን።
“እቴጌ ኸግማርዳ ጥዱ አይሻልም ኑሯል?” ይላታል አንዱ ግንበኛ።
“ግማርዳ ነው እንጂ ለንድህ ያለው” ይላል ሌላው።
“ሁሉም ለመጡበት ጉዳይ ያገልግላሉ” ይላሉ እናትና ልጅ።
ሠራተኞቹ ነገሥታቱ ከእነሱ ጎን ሆነው መሥራታቸው፣ የእነሱን ሐሳብ መስማታቸው አስደነቃቸው። እንደ ሰማይ ከዋክብት ሩቅ የመሰሏቸው፣ ብሎም እንደነሱ ከስጋና ከደም የተሰሩ የማይመስሏቸው የነበሩት ነገሥታት ሰው ሆነው አገኟቸው። በተለይም ደግሞ ኢያሱ ራሱ ሥራው ላይ ተሰማርቶ ከእነሱ እኩል ሲቀባና ሲሠራ አይተው
ተደመሙ።
ወትሮውንም ማንም ፍርድ ፈላጊ ሰተት ብሎ ቤተመንግሥት ገብቶ
እንዲዳኝ ስላደረገ፣ ፍትሕ ለጎደለበት ፍትሕ ስለሰጠና ለድኃ ስለቸረ ይወዱትና ይሳሱለት ነበረና እንደዚህ በቅርብ ከነሱ ጋር ሲሠራ ሲያዩት ይበልጥ ወደዱት።
አንድ ጠዋት ሠራተኞቹ በግብር አዳራሹ አንድ ወገን ላይ እየተሠራ
ስላለው ረጅም የእንቁላል ቅርጽ ያለው ግንብ ድምጻቸውን ዝቅ
አድርገው ያወራሉ። ምንትዋብና ኢያሱ ጎን ለጎን ቆመው የተሠራውን ሥራ ይመለከታሉ።
“አላየህም እንዴ ኸዛ ላይ ሁነህ? ቀሀ እኮ ወለል ብሎ ይታያል” አለ፣
አንዱ ግንበኛ።
“ቀሀ ትላለህ? ጣና ይታይ የለ? ቀሀማ ኸዝሁ ነው።” ከት ብሎ ሳቀ ሌላው።
“ጣና ይታያል ነው ምትሉት?” አለች ምንትዋብ፣ በመገረም።
“አዎ እቴጌ ሲያልቅ ያዩታል። እንዲያው ጣና ወለል ብሎ ነው
ሚታይ” ኣላት፣ አንደኛው ግንበኛ።
“እስቲያልቅ ምን አቆየን፣ አሁን አናየውም?” አላት ኢያሱ።
እናትና ልጅ ፎቁ ላይ ወጡ።
“ውነት ነው ኢያሱ። ያውልህ ... ያ ሚታየው ጣና እኮ ነው። ይኸማ
ለጥበቃ አይሆንም። ለኔ ነው ሚሆን” አለችው።
“ውነትም ወለል ብሎ ይታያል። ቀሀም ይኸው። ውነትሽ ነው።
ላንቺ ይሆናል። ዐጥሩ ተሠርቶ ሲያልቅ ቁስቋም ፊት ለፊት እንደ
ተደረገው የጥበቃ ሰቀላዎቹ ዙርያውን ይሠራሉ።”
ምንትዋብ ደስ አላት። እንዴት እሰተ ዛሬ አላሰብሁትም ብላ
ተገረመች። የተመረጡ እንደ ግራዝማች ኢያሱ፣ ሮብዓምና ሌሎችም እንግዶች መቀበያና ለራሷም መዝናኛ እንደምታደርገው ወሰነች።
አንድ ቀን፣ ምንትዋብ አፄ ፋሲለደስ ቤተመንግሥት ልጇ ኢያሱጋ ለመሄድ፣ በልዩ ልዩ ጌጣ ጌጥ የተሸለመችው በቅሎዋ ላይ ተቀምጣ፣የእሷና የኢያሱ መግቢያና መውጫ ብቻ በሆነው በር ከዐጀቧ ጋር እንደ ሁልጊዜው ባለ ወርቀ ዘቦ ድባብ ተይዞላት ከግቢ ወጣች።
ቤተመንግሥት ስትገባ እንደወትሮው ሁሉም ሰገዱላት። ወደ ኢያሱ መኖሪያ አመራች። ኢያሱ ወጥቶ በደስታ ተቀበላትና ውስጥ ገብተው ጨዋታ ጀመሩ። ኢያሱ ልትነግረው የምትፈልገው ነገር ሲኖር ያውቃል። ምን ልትነግረው፣ ወይንም ምን ልትጠይቀው እንደፈለገች
በጉጉት መጠበቅ ለምዷል።
“ኢያሱ ዛሬ የመጣሁት” አለችው፣ በመጨረሻ። “አንድም አንተን
ለማየት ሌላም ቀደም ብሎ እንደተነጋገርነው ቃሮዳና ዙርያውን
የተተከለው ወይን እንዴት እንዳፈራ ልነግርህ ነው። ትናንት ይዘው
መጡ፤ መቸስ ጉድ ትላለህ። እንዳው ማማሩን ብታይ ጉድ ትላለህ።”
“እንዴት እንደዝኸ ተሎ ደረሰ?”
“ደረሰ። ይገርምሀል። እና አሁን የግብር ቤቱም ሥራ እያለቀ ነው።
ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ግብሩን በሰፊው እናርግላቸው።የስተዛሬው እንዳው በቂ ከልነበረም።”
“እናርግላቸው እንጂ አሁንማ። ምን እንጠብቃለን?”
“ወይኑ መጠመቅ እንዲጀምር ትዛዝ ሰጥቻለሁ።”
“መልካም ነው።”
ጥቂት ስለቤተመንግሥት ጉዳይ ከተወያዩ በኋላ ተነስታ ወጣች።
ከወራት በኋላ፣ አንድ ቅዳሜ ዳግማዊ ኢያሱ ማለዳ ላይ ቁስቋም መጣ።ሰማዩ ጥርት ብሏል። ፀሐይዋ ደምቃለች። ምንትዋብ ከቤተመንግሥቷ
በደረጃ ወጥታ ተቀበለችው። እያወሩ ቁልቁል ሲወርዱ ተሰርቶ
ያለቀውን የግብር አዳራሽ አይታ ንግግሯን አቋርጣ፣ “ኢያሱ እይልኝ!ጉድ በልልኝ! እይልኝ እንዴት እንደሚያምር!” አለችው። በደስታ እንደ ልጅ በጨፈረች ደስ ባላት፣ የቤተመንግሥት ሥርዐትና ዕድሜ አልፈቅድ ብለዋት እንጂ።
“ውነትሽ ነው ያምራል! ሁለዜ ስለምናየው እስታሁን እንደዝኸ
እንደዛሬው ማማሩን አላወቅነም እኮ።”
ምንትዋብ ቀልቧ ግንቡ ላይ ነው። አልሰማችውም።
በተጠጋች ቁጥር የግንቡ ግርማ ሞገስ አስደነቃት። የአሠራሩ ጥራት፣የልስኑ ማማርና መርቀቅ፣ የቀለሙ ውበት ከገመተችው በላይ ሆነባት።
ኣጠገቡ ሲቆሙ ስሜቷ አሽነፋትና እንባዋ ዱብ ዱብ አለ።
ከኋላቸው የቆሙት የቤተመንግሥት ባለሟሎች፣ ሠዓሊዎች፣ሮብዓም፣ ካህናትና ሊቃውንት አዳራሹን በአድናቆት ተመለከቱ።
ሁሉም በአንድ ላይ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “እዝጊሃር ያክብራችሁ።
የናንተ ሥራ ነው” እያሉ አመሰገኗቸው።ምንትዋብ መናገር ተስኗት የለም የለም የሁሉም ነው። ሰው ተረባርቦ ነው ይኸን መሳይ ታላቅ ሥራ የሠራው። ሁሉም ይመሰገናል። የሠሩትን
ሁሉ ትናንትም አመስግኛቸዋለሁ። ያለኝን ሁሉ ሰጥቻለሁ። እዝጊሃር
ያክብራቸው አለች፣ ለራሷ። ራሴን ማመስገን አይሁንብኝና ልክ
እንዳልሁት፣ ልክ በሰጠሁት አሳብ መሠረት እኮ ነው የተሠራ አለች።
ባልስን፣ በቀለም ምርጫና በአጠቃላይ ላይ አሻራዋን የጣለችበትን ግንብ እያየች።
በስተቀኝ በኩል ወደ ላይ የወጣውን እንቁላል ግንብ አይታ፣ እሱስ ቢሆን እንዴት አምራል? ኸ'ያሱ ጋር እንደልብ ቁጭ ብሎ ለማውራት ይመቻል አለች፣ በአደባባይ እንደልብ መገናኘት ሰለማይችሉት ስለ
ግራዝማች ኢያሱ አስባ። ኸመላከ ጠሐይ ሮብዓምም ጋር ጥሩ ወግ
መያዝ እችላለሁ ኸዝያ አለች።
ፊቷን ወደ ልጇ መልሳ፣ “ኢያሱ ኸላይ እግንቡ ላይ በግራ በኩል
ያሉትን የመስቀል ቅርጦች አየኻቸው? ቀጥሎ ያለውንስ ዘውድ?”
“ሁሉም ቁልጭ ብለው ይታያሉ። አየሽው ከጎኑ ያለውን በጉን
ሲገድል ሚታየው አንበሳ? ኸጎኑ አንበሳ ላይ የተቀመጠውስ ንጉሥ ያገራችን ምልክት! እንዴት ጥሩ ወጥቷል። ቀጥሎ ያሉት ዝሆንና
አንበሳስ እንዴት እንዳማሩ አየሽ?”
“አዎ ልክ አንተ እንዳልኸው ነው የተሠሩት። የጣድቁ የአባ
ሳሙኤልና የአቡነ ዮሐንስ ምስሎችስ ቢሆኑ እንዴት እንዳማሩ” አለች፣
የዋልድባውን መነኩሴ የአባ ሳሙኤልንና የዐዲሱን አቡን የዮሐንስን ምስል እየተመለከተች።
ራሷን አረጋግታ ዙርያውን ቃኘች። አስቀድማ ያሰበችው ሐሳብ
ሥራ ላይ የሚውልበት ሰዐት
ተቃርቧል።ወደ ኢያሱ ዞረች።
“ኢያሱ ኸዝኸ ኻዳራሹ በስተግራ በኩል ኻሰብሁት በላይ በቂ መሬትአለ። የሴቶች ሙያ ተማሪ ቤት ማሳነጽ ፈልጋለሁ ብዬ ማልነበር? ያውልህ ኸጠሎት ቤቱ ዠርባ ዋርካው አጠገብ ደሞ ሌላ ሰፊ መሬት።እሱም ቢሆን እንዳሰብሁት...”
“ምን አስበሽለት ነበር ለቦታው?”
👍15
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....የሕዳር ቁስቋም ዕለት ነው። ምንትዋብ ትልቅ ግብር ጥላለች። ምግቡም፣ወይን ጠጁም፣ ጠጁም፣ አረቄውም በገፍ ተዘጋጅቷል። አስቀድማ፣
ዛሬ ሊቃውንቱና ካህናቱ ከገቡ ወዲያ ዋናውን ሆነ የስርቆሹን በር
እንድትዘጉ። የወይን ጠጅም እየደጋገማችሁ እንድትሰጧቸው” ብላ ትዕዛዝ አስተላልፋለች።
“ይኸ ሁሉ ስለምንድርነው?” ሲል ጠየቃት፣ ኢያሱ።
“ዛሬ ካህናቱንና ሊቃውንቱን ጉድ ሠራለሁ።”
“እንዴት አርገሽ... ደሞስ ስለምን?”
“እነሱ ሁልግዝየ በቅኔው፣ በተረትና ምሳሌውና በመጠጥ ያቸንፉኛል።
ዛሬ ግን እኔ አቸንፋቸዋለሁ ብዬ ተነስቻለሁ።”
ሳቀ ኢያሱ ።
ከቅዳሴ በኋላ፣ ከየደብሩ የተጋበዙት ካህናትና ሊቃውንት ወደ ቤተመንግሥት ተመሙ። ሠዓሊዎችና ሙዚቀኞችም ጎረፉ። የግብር ሥርዐት ተጠብቆ ምግብ ተበላ። የወይን ጠጅ ተቀዳ ። የካህናቱና የሊቃውንቱ ዋንጫ ሲጎድል አጋፋሪዎች በታዘዙት መሠረት እየተመላለሱ ሞሉ።
እንግዶቹ ፊኛቸው አስቸገራቸው። ሊወጡ ፈልገው ቢነሱ ከፊት
ከኋላ በሩ ዝግ ነው። የሚከፍት የለም። ተጨነቁ፤ ተጠበቡ። እየተያዩ መቅበጥበጥ ብቻ ሆነ። በመጨረሻ መለኛው ሊቅ አለቃ ኢሳያስ ተነሥተው እናትና ልጁን እጅ ነሱና፣ “እቴጌ አንድ ነገር እንድጠይቅ ይፈቀድልኝ” አሏት።
“ይበሉ ይጠይቁ።”
“እቴጌ አምስት መቶና አምስት መቶ ስንት ነው?”
ያልጠርጠረችው ምንትዋብ፣ “ምን ያለ ጥያቄ ነው? ይኸ ሊያቅተኝ? ሽ ነዋ!” አለች።
አለቃ ኢሳያስ፣ “እቴጌ “ሽናዋ' ብለዋል” ሲሉ ያ ፊኛው አስጨንቆት የነበረ ሊቅና ካህን ሁሉ የተቀመጠበትን ከህንድ ሃገር የመጣ ስጋጃ አረሰረሰ።
ምንትዋብ በመሸነፏ ሳቀች፣ ተንኮሏ እንዳልሠራ ተገነዘበች።
በእርግጥም ሊቃውንቱን ማሸነፍ እንደማትችል ተገነዘበች። አለቃ
ኢሳያስን ለብልሐታቸው ሽለመቻችው። አዲሱ የግብር ኣዳራሽም በሕዝብ ዘንድ “ሽናዋ” የሚል ስያሜ አተረፈ።
ከሽናዋ በኋላ፣ የሴቶች ሙያ ትምህርት ቤቱ ግንባታ ተጀመረ።
ግንባታው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ሴቶች ተመርጠው እንደ
ፈትል ያሉ ልዩ ልዩ የእጅ ጥበባትና ዶሮ መገነጣጠል እንዲማሩ ሆነ።
ተማሪዎቹ ዶሮ አስራ ሁለት ብልት እንዳላት አወቁ። ፊደልና የቁም
ጽሕፈት እንዲከታተሉ ተደረገ። ምንትዋብ ልትጎበኛቸው በሄደች
ቁጥር በሙያና በትምህርት በርትተው እንዲማሩ አስጠነቀቀች።ከዓመታት በፊት አያቷ የነገሥታት ዝርያዎች ወህኒ ይላካሉ እዛው አርጅተው ይሞታሉ፣ ብለው ሲነግሯት፣ “ክፉ ነገር። እኼማ መሆን የለበትም” እንዳለችው ከጸሎት ቤቷ በስተቀኝ በኩል የአፄ በካፋ ዘመዶች ሆኑ የሌላ ነገሥታት ዝርያዎች ወይንም የራሷ ዘመዶች መኖሪያና መማርያ የሚሆን ህንፃ አሠርታ፣ ልጆቹ ወህኒ አምባ በእግር
ብረት ታስረው ከመማቀቅ ይልቅ ፊደል፣ የቁም ጽሕፈትና ፍትሖ
ነገሥት እንዲማሩ ሆነ።
ምንትዋብና ኢያሱ ስማቸው ከአጥናፍ አጥናፍ ገነነ።
ምንትዋብና ዳግማዊ ኢያሱ ስማቸው ቢገንም፣ አልፎ ኣልፎም ቢሆን በመኳንንቱ ዘንድ “ቋረኞች” ላይ ጥርጣሬ ስላለ፣ ምንትዋብም ብትሆን ያለነሱ ድጋፍ ርቃ እንደማትሄድ ስለምታውቅ በጉዳዩ ከኢያሱ ጋር መምከር ፈለገች።
“ኢያሱ እንዳው አንድ ነገር ላጫውትህ ብየ” አለችው፣ አንድ ቀን እንቁላል ግንብ ውስጥ ተቀምጠው እየተጫወቱ ሳለ።
“ምን ነገር?”
“እንደምታውቀው “ቋረኞች” ሚሉ ዘይቤ እንደ ዱካ ይከተለናል።
ሥልጣኑን ሁሉ ቋረኞች ይዘውታል ይላሉ። ይሰንብት እንጂ ቀን
ጠብቀው በኛ ላይ መነሳታቸው አይቀርም። የጎዣም፣ የትግሬ፣
የቤገምድርና የስሜን መኳንንት ዋዛ ማዶሉ። ይመስገነው እስታሁን ሰላም ነን። ወደ ፊት ግን እንጃ ሰላማችን ሊደፈርስ ይችላል ብየ ሰጋለሁ።ሰላም ማጣት ብቻ ሳይሆን አልጋውን ሊፈታተኑ ይችላሉ። የወህኒዎቹ
እንደሆኑ ዐይናቸው መቸም ግዝየ ኻልጋው ላይ ተነስቶ አያውቅም።
ተዘጋጅቶ መቀመጡ አይከፋም። ሥልጣን አይበቃቸው፣ ጉልት፣
ርስትና ርስተ ጉልት ለስንቱ መኳንንት ሰጠን። አይጠቅማቸውም።ኢያሱ ጥቂቱ እኮ ነው ላገሬ ሚለው። ኻለነሱ ድጋፍ ደሞ አይሆን።እነሱን ለማስታገስ ስንቱን ድሬ ጨረስሁ። አሁንም ቢሆን አርቀን ማሰብ አለብን። ነገ አንዱ ቢነሳ አጋዥ ያስፈልገናል። እና አሳቤ ምን
መሰለህ ይኸ የስሜን፣ የጎዣም፣ የቤገምድርና የትግሬ ባላባት ሁሉ
ቀልቡን ሰብስብ እንዲያረግ ወሎዎች ጠንካራ ጦር አላቸውና ኸነሱ ጋር በጋብቻ ብንተሳሰር ምን ይመስልሀል?”
“ኣሳብሽ መልካም ነው። ማነን ልታጋቢ አሰብሽ?”
“አንተን።”
“እኔን?” ከት ብሎ ሳቀ።
“አዎ አንተን:: ብዙ አስቤበት ነው። አሁን ኸወሎች ጋር መጋባት
ያስፈልጋል። የልገሮችህ እናት...” ዕቁባት ሆና ትቀመጣለች ማለት
ፈልጋ ዝም አለች።?
“እና እኔን ኸማን ልታጋቢ ነው?” አላት፣ ዝም ስትል ።
“ውቢት ምትባል የወሎ ባላባት ልዥ አለች። አጠያይቄ አለላ ናት
አሉ። ብቻ የወሎ ልዥ ስለሆነች በድብቅ መሆን አለበት።”
ኢያሱ ስለመኳንንቱ ያለችው አሳስቦት ነበርና ዝም አለ። ምንትዋብ ዝምታውን እንደ እሺታ ቆጠረች።
ብዙም ሳይቆይ ምንትዋብ የወሎ ባላባት ልጅ የሆነችውን ውቢትን
ከኢያሱ ጋር አጋባች። ውቢትን ክርስትና አስነስተው ወለተቤርሳቤሕ አሰኝተው፣ የመኳንንቱን ጉምጉምታ ለማቀዝቀዝ በድብቅ ኣስቀመጡ።
ውቢት ኢዮአስ የተባለ ወንድ ልጅ ወለደች።
ምንትዋብና ኢያሱ ምንም እንኳን ራስ ቢትወደድ ወልደልዑል
መንግሥታቸውን ከዘመዶቹ ጋር አስከብሮና አጠናክሮ ቢይዝላቸውም፣ባላባቶች ከወሎ በማምጣት ሥልጣን ላይ አስቀመጡ። ሲያንገራግር
የነበረውን የጎጃሙን ባላባት ዮሴድቅን ደግሞ፣ ደጃዝማች ብለው፣ይዞታውን ጨምረው፣ በኋላ ሞጣ ጊዮርጊስን የደበረችውን ወለተእስራኤልን ድረውለት አረጋጉት።
እናትና ልጅ ያሰቡትን ሥራ ላይ ከማዋል አልቆጠብ አሉ። በተለይም ኢያሱ ለአትክልት ቦታ ልዩ ፍቅር ስለነበረው፣ ጐንደርን አፀድ በአፀድ አደረጋት። ሎሚና ሌሎች ፍሬዎች ጐንደርን የመዓዛ ባለፀጋ አደረጓት።
አብያተ ክርስቲያናትን በጭልጋ፣ አለፋ ጣቁሳና ጐንደር በኖራ
አሠሩ። ሌሎችን አሳደሱ። ጣና ሐይቅ በታንኳ እየተመላለሱ ኢያሱ
ክብራን ገብርኤልን ሲያሳድስ፣ እሷ ደቅ ውስጥ “ስሞት እቀበርበታለሁ” ያለችውን ናርጋ የኛ - ሥላሤን በጡብና በጐንደርኛ ይዘት አሠራች። ናርጋ ሥላሤን ስታሠራ፣ ሥሙር የተባለውን የራሷን ምስል የላከላትን ሠዓሊ አስታወሰች። እንዴት ሊገኝ እንደሚችል አሰበች።ሌሎች ሠዓሊዎች በሥዕል ሥራው ተሳተፉ። ናርጋ ሥላሤ በሥዕል
አሸበረቀች። ምንትዋብ አክብሮቷን ለመግለፅ ከማርያምና ከክርስቶስ
እግር ሥር የራሷን ምስሎች አሠራች። አብያተ ክርስቲያናቱ የሥዕል ባለቤት ሆኑ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ “ብዙው መጻሕፍት ወደ ክብራን ገብርኤል
እንዲሄዱ ፈቃዴ ነው” ባለው መሠረት ከተለያዩ የሃገሪቱ ከፍሎች የተሰበሰቡ በሺህ የሚቆጠሩ መጻሕፍት ክብራን ገብርኤል ገብተው
ተቀመጡ።
“አንተ ደሞ ሁሉ ነገር ወደዛ እንዲኸድ ትፈልጋለህ” ብላ ፈገግ
አለች፣ ምንትዋብ አንድ ቀን። ቀጠል አድርጋ፣ “ለየደብሩ እኩል
ማከፋፈል ነው እንጂ” አለችው።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....የሕዳር ቁስቋም ዕለት ነው። ምንትዋብ ትልቅ ግብር ጥላለች። ምግቡም፣ወይን ጠጁም፣ ጠጁም፣ አረቄውም በገፍ ተዘጋጅቷል። አስቀድማ፣
ዛሬ ሊቃውንቱና ካህናቱ ከገቡ ወዲያ ዋናውን ሆነ የስርቆሹን በር
እንድትዘጉ። የወይን ጠጅም እየደጋገማችሁ እንድትሰጧቸው” ብላ ትዕዛዝ አስተላልፋለች።
“ይኸ ሁሉ ስለምንድርነው?” ሲል ጠየቃት፣ ኢያሱ።
“ዛሬ ካህናቱንና ሊቃውንቱን ጉድ ሠራለሁ።”
“እንዴት አርገሽ... ደሞስ ስለምን?”
“እነሱ ሁልግዝየ በቅኔው፣ በተረትና ምሳሌውና በመጠጥ ያቸንፉኛል።
ዛሬ ግን እኔ አቸንፋቸዋለሁ ብዬ ተነስቻለሁ።”
ሳቀ ኢያሱ ።
ከቅዳሴ በኋላ፣ ከየደብሩ የተጋበዙት ካህናትና ሊቃውንት ወደ ቤተመንግሥት ተመሙ። ሠዓሊዎችና ሙዚቀኞችም ጎረፉ። የግብር ሥርዐት ተጠብቆ ምግብ ተበላ። የወይን ጠጅ ተቀዳ ። የካህናቱና የሊቃውንቱ ዋንጫ ሲጎድል አጋፋሪዎች በታዘዙት መሠረት እየተመላለሱ ሞሉ።
እንግዶቹ ፊኛቸው አስቸገራቸው። ሊወጡ ፈልገው ቢነሱ ከፊት
ከኋላ በሩ ዝግ ነው። የሚከፍት የለም። ተጨነቁ፤ ተጠበቡ። እየተያዩ መቅበጥበጥ ብቻ ሆነ። በመጨረሻ መለኛው ሊቅ አለቃ ኢሳያስ ተነሥተው እናትና ልጁን እጅ ነሱና፣ “እቴጌ አንድ ነገር እንድጠይቅ ይፈቀድልኝ” አሏት።
“ይበሉ ይጠይቁ።”
“እቴጌ አምስት መቶና አምስት መቶ ስንት ነው?”
ያልጠርጠረችው ምንትዋብ፣ “ምን ያለ ጥያቄ ነው? ይኸ ሊያቅተኝ? ሽ ነዋ!” አለች።
አለቃ ኢሳያስ፣ “እቴጌ “ሽናዋ' ብለዋል” ሲሉ ያ ፊኛው አስጨንቆት የነበረ ሊቅና ካህን ሁሉ የተቀመጠበትን ከህንድ ሃገር የመጣ ስጋጃ አረሰረሰ።
ምንትዋብ በመሸነፏ ሳቀች፣ ተንኮሏ እንዳልሠራ ተገነዘበች።
በእርግጥም ሊቃውንቱን ማሸነፍ እንደማትችል ተገነዘበች። አለቃ
ኢሳያስን ለብልሐታቸው ሽለመቻችው። አዲሱ የግብር ኣዳራሽም በሕዝብ ዘንድ “ሽናዋ” የሚል ስያሜ አተረፈ።
ከሽናዋ በኋላ፣ የሴቶች ሙያ ትምህርት ቤቱ ግንባታ ተጀመረ።
ግንባታው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ሴቶች ተመርጠው እንደ
ፈትል ያሉ ልዩ ልዩ የእጅ ጥበባትና ዶሮ መገነጣጠል እንዲማሩ ሆነ።
ተማሪዎቹ ዶሮ አስራ ሁለት ብልት እንዳላት አወቁ። ፊደልና የቁም
ጽሕፈት እንዲከታተሉ ተደረገ። ምንትዋብ ልትጎበኛቸው በሄደች
ቁጥር በሙያና በትምህርት በርትተው እንዲማሩ አስጠነቀቀች።ከዓመታት በፊት አያቷ የነገሥታት ዝርያዎች ወህኒ ይላካሉ እዛው አርጅተው ይሞታሉ፣ ብለው ሲነግሯት፣ “ክፉ ነገር። እኼማ መሆን የለበትም” እንዳለችው ከጸሎት ቤቷ በስተቀኝ በኩል የአፄ በካፋ ዘመዶች ሆኑ የሌላ ነገሥታት ዝርያዎች ወይንም የራሷ ዘመዶች መኖሪያና መማርያ የሚሆን ህንፃ አሠርታ፣ ልጆቹ ወህኒ አምባ በእግር
ብረት ታስረው ከመማቀቅ ይልቅ ፊደል፣ የቁም ጽሕፈትና ፍትሖ
ነገሥት እንዲማሩ ሆነ።
ምንትዋብና ኢያሱ ስማቸው ከአጥናፍ አጥናፍ ገነነ።
ምንትዋብና ዳግማዊ ኢያሱ ስማቸው ቢገንም፣ አልፎ ኣልፎም ቢሆን በመኳንንቱ ዘንድ “ቋረኞች” ላይ ጥርጣሬ ስላለ፣ ምንትዋብም ብትሆን ያለነሱ ድጋፍ ርቃ እንደማትሄድ ስለምታውቅ በጉዳዩ ከኢያሱ ጋር መምከር ፈለገች።
“ኢያሱ እንዳው አንድ ነገር ላጫውትህ ብየ” አለችው፣ አንድ ቀን እንቁላል ግንብ ውስጥ ተቀምጠው እየተጫወቱ ሳለ።
“ምን ነገር?”
“እንደምታውቀው “ቋረኞች” ሚሉ ዘይቤ እንደ ዱካ ይከተለናል።
ሥልጣኑን ሁሉ ቋረኞች ይዘውታል ይላሉ። ይሰንብት እንጂ ቀን
ጠብቀው በኛ ላይ መነሳታቸው አይቀርም። የጎዣም፣ የትግሬ፣
የቤገምድርና የስሜን መኳንንት ዋዛ ማዶሉ። ይመስገነው እስታሁን ሰላም ነን። ወደ ፊት ግን እንጃ ሰላማችን ሊደፈርስ ይችላል ብየ ሰጋለሁ።ሰላም ማጣት ብቻ ሳይሆን አልጋውን ሊፈታተኑ ይችላሉ። የወህኒዎቹ
እንደሆኑ ዐይናቸው መቸም ግዝየ ኻልጋው ላይ ተነስቶ አያውቅም።
ተዘጋጅቶ መቀመጡ አይከፋም። ሥልጣን አይበቃቸው፣ ጉልት፣
ርስትና ርስተ ጉልት ለስንቱ መኳንንት ሰጠን። አይጠቅማቸውም።ኢያሱ ጥቂቱ እኮ ነው ላገሬ ሚለው። ኻለነሱ ድጋፍ ደሞ አይሆን።እነሱን ለማስታገስ ስንቱን ድሬ ጨረስሁ። አሁንም ቢሆን አርቀን ማሰብ አለብን። ነገ አንዱ ቢነሳ አጋዥ ያስፈልገናል። እና አሳቤ ምን
መሰለህ ይኸ የስሜን፣ የጎዣም፣ የቤገምድርና የትግሬ ባላባት ሁሉ
ቀልቡን ሰብስብ እንዲያረግ ወሎዎች ጠንካራ ጦር አላቸውና ኸነሱ ጋር በጋብቻ ብንተሳሰር ምን ይመስልሀል?”
“ኣሳብሽ መልካም ነው። ማነን ልታጋቢ አሰብሽ?”
“አንተን።”
“እኔን?” ከት ብሎ ሳቀ።
“አዎ አንተን:: ብዙ አስቤበት ነው። አሁን ኸወሎች ጋር መጋባት
ያስፈልጋል። የልገሮችህ እናት...” ዕቁባት ሆና ትቀመጣለች ማለት
ፈልጋ ዝም አለች።?
“እና እኔን ኸማን ልታጋቢ ነው?” አላት፣ ዝም ስትል ።
“ውቢት ምትባል የወሎ ባላባት ልዥ አለች። አጠያይቄ አለላ ናት
አሉ። ብቻ የወሎ ልዥ ስለሆነች በድብቅ መሆን አለበት።”
ኢያሱ ስለመኳንንቱ ያለችው አሳስቦት ነበርና ዝም አለ። ምንትዋብ ዝምታውን እንደ እሺታ ቆጠረች።
ብዙም ሳይቆይ ምንትዋብ የወሎ ባላባት ልጅ የሆነችውን ውቢትን
ከኢያሱ ጋር አጋባች። ውቢትን ክርስትና አስነስተው ወለተቤርሳቤሕ አሰኝተው፣ የመኳንንቱን ጉምጉምታ ለማቀዝቀዝ በድብቅ ኣስቀመጡ።
ውቢት ኢዮአስ የተባለ ወንድ ልጅ ወለደች።
ምንትዋብና ኢያሱ ምንም እንኳን ራስ ቢትወደድ ወልደልዑል
መንግሥታቸውን ከዘመዶቹ ጋር አስከብሮና አጠናክሮ ቢይዝላቸውም፣ባላባቶች ከወሎ በማምጣት ሥልጣን ላይ አስቀመጡ። ሲያንገራግር
የነበረውን የጎጃሙን ባላባት ዮሴድቅን ደግሞ፣ ደጃዝማች ብለው፣ይዞታውን ጨምረው፣ በኋላ ሞጣ ጊዮርጊስን የደበረችውን ወለተእስራኤልን ድረውለት አረጋጉት።
እናትና ልጅ ያሰቡትን ሥራ ላይ ከማዋል አልቆጠብ አሉ። በተለይም ኢያሱ ለአትክልት ቦታ ልዩ ፍቅር ስለነበረው፣ ጐንደርን አፀድ በአፀድ አደረጋት። ሎሚና ሌሎች ፍሬዎች ጐንደርን የመዓዛ ባለፀጋ አደረጓት።
አብያተ ክርስቲያናትን በጭልጋ፣ አለፋ ጣቁሳና ጐንደር በኖራ
አሠሩ። ሌሎችን አሳደሱ። ጣና ሐይቅ በታንኳ እየተመላለሱ ኢያሱ
ክብራን ገብርኤልን ሲያሳድስ፣ እሷ ደቅ ውስጥ “ስሞት እቀበርበታለሁ” ያለችውን ናርጋ የኛ - ሥላሤን በጡብና በጐንደርኛ ይዘት አሠራች። ናርጋ ሥላሤን ስታሠራ፣ ሥሙር የተባለውን የራሷን ምስል የላከላትን ሠዓሊ አስታወሰች። እንዴት ሊገኝ እንደሚችል አሰበች።ሌሎች ሠዓሊዎች በሥዕል ሥራው ተሳተፉ። ናርጋ ሥላሤ በሥዕል
አሸበረቀች። ምንትዋብ አክብሮቷን ለመግለፅ ከማርያምና ከክርስቶስ
እግር ሥር የራሷን ምስሎች አሠራች። አብያተ ክርስቲያናቱ የሥዕል ባለቤት ሆኑ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ “ብዙው መጻሕፍት ወደ ክብራን ገብርኤል
እንዲሄዱ ፈቃዴ ነው” ባለው መሠረት ከተለያዩ የሃገሪቱ ከፍሎች የተሰበሰቡ በሺህ የሚቆጠሩ መጻሕፍት ክብራን ገብርኤል ገብተው
ተቀመጡ።
“አንተ ደሞ ሁሉ ነገር ወደዛ እንዲኸድ ትፈልጋለህ” ብላ ፈገግ
አለች፣ ምንትዋብ አንድ ቀን። ቀጠል አድርጋ፣ “ለየደብሩ እኩል
ማከፋፈል ነው እንጂ” አለችው።
👍11
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ከንስሐ ስትወጣ መቅሰፍት ተከተላት። እሷና ኢያሱ በነገሡ በአስራ ስድስተኛ ዓመታቸው ላይ አንድ ጠዋት ምንትዋብ ወደ ጸሎት ቤት ልትሄድ ስትዘጋጅ፣ አንደኛዋ ደንገጡሯ መጥታ፣ “ኧረ እቴጌ ሰማይ ምድሩ ዕርድ መስሏል” አለቻት፣ ቢጫ ስለለበሰው ሰማይና መሬት።
“እንዴት?”
“እንዲህ ዕርድ ሲመስል በነገታው አንበጣ ይወራል አሉ። ደሞም
ንፋስ እየነፈሰ ነው፣ ሰማዩም ደመና አዝሏል። ሁለቱም ነገሩን
ያባብሱታል።”
ፈጠን ብላ ወደ መስኮቱ ሄደች ምንትዋብ። እውነትም የጐንደር
ሰማይ ቢጫ ሆኗል። አፏን በእጇ ይዛ፣ “ምን ጉድ ነው? ምን ይሻላል?” አለች።
“እግዚኦ ማለት ነው እንጂ ሌላ ምን አለ?” አለች፣ ደንገጡሯ።
ኢያሱ መቸም ይሰማል... ይነግሩታል ኣለች ምንትዋብ፣ ለራሷ።
ካህናቱ በፍጥነት ጸሎት እንዲይዙ መልዕክት ላከችባቸው። ጸሎት
ቤቷ ለመሄድ ወጥታ ተመልሳ እልፍኟ ተቀመጠች። ሰማይና ምድሩ እንደዛ ሆኖ ስታየው አስፈራት።
በማግሥቱ የአንበጣ መንጋ ሰማዩን አለበሰው። የአንድ ቀን ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀናት በመቆየቱ ቤተመንግሥትም ጐንደርም ተጨነቁ፤ተጠበቡ። ሕዝቡ፣ “እግዚኦ” አለ። ታላቅ መቅሰፍት እንደመጣ አመነ።
ምሽት ላይ ሳይቀር አንበጦች ሰማዩን አንለቅ አሉ። ከባድ ዝናብና
ንፋስ ወረራውን አባባሱት።
ውሎ አድሮም ሰብል ተበላሽ። እየቆየ ሲሄድ ጐንደር ትልቅ ችግር
ላይ ስትወድቅ፣ ሕዝቧንና እንስሳዋን ረሐብ አጠወለገው፤ በሽታ አጣደፈው። ቀናትና ወራት እያለፉ ሲመጡ ቀባሪ እስኪጠፋ ሙታን በየወደቁበት ቀሩ። የተረፉት ከነገሥታቱ ጀምሮ በኃይለኛ ጉንፋን ተያዙ። እንዲህ እያለ ሁለት ዓመት አለፈ።
ሰዉ ካደረሰበት ጉዳት ገና ሳያገግም፣ ተምች በመመለሱ ችግር ብቻ ሳይሆን፣ ከቀድሞው የበለጠ ረሐብ ገባ።
ጌታችን ወርዶ ከባሕር፣
ኣዳምን ዋና ሊያስተምር፣
አፋፍ ላይ ሁነን ብናየው፣
እያጣ አለቀ ሰው።
ተብሎ እንደተገጠመው ሁሉ ጐንደርን ጨምሮ በደጋም በቆላም ሰው አለቀ። ከቤተመንግሥት የተቻለውን ያህል የእህል እርዳታ ቢደረግ እያደር ዐቅም አነሰ። የቻለ ጐንደርና አካባቢዋን ጥሎ ተሰደደ ::መሬቱን፣ ንብረቱንና ደብሩን ጥሎ መሄድ ያልሆነለት ለረሐብና ለበሽታ ተጋለጠ።
ጐንደሬዎች የሕይወት ምልክቱ ከፊታቸው ላይ ጠፍቶ ባዶው ላይ
አፈጠጡ። ከንፈራቸው ሐሩርና ውርጭ የመታው ይመስል ከስሞ፣
ቆዳቸው ተሰነጣጥቆ፣ የአንገታቸው ቆዳ ተንጠልጥሎ፣ የጉንጫቸው አጥንት አፈንግጦ፣ የሰለሉ እጆችና እግሮቻቸውን ማንሳት ተስኗቸው በረሐብ፣ በጥምና በበሽታ ተንጠራወዙ።
መከራ በሰዎች ገጽታ ላይ ግዘፍ ነሥቶ ታየ።
ለእናት፣ ለአባትና ለልጅ ቀባሪ የሚሆን ዐቅም ጠፍቶ ጐንደሬዎች
ዐይናቸው ቦዞ፣ እንባቸው ደርቆ፣ እጅና እግራቸው ዝሎ ተቀመጡ።
ትናንት ስቀው፣ ወደው፣ ጠልተው ከቶውንም በልተው የማያውቁ
መሰሉ። ዛሬ ተስፋቸውን ተነጥቀው ከሞት ጋር ተፋጠጡ። ነገ የእነሱ እንዳልሆነች አውቀው እጃቸውን ለሞት ሰጡ።
ሞት፣ ያ የሰው ልጅ የቁም ቅዠት አላስደነግጥ አለ። እንደተራ
ነገር ተቆጠረ። ጐንደሬዎች የሚዘክራቸው መላዕክትና ቅዱሳን ሁሉ ወዴት እንደሄዱ ጠየቁ። የእግዚአብሔርንም መኖሪያ አጠያየቁ። እንደ ዳዊት፣ “ጆሮን የፈጠረ አይሰማምን? ዐይንን የፈጠረ አያይምን?” ብለው
አቤቱታ አስገቡ። ሕጻናት ጡት አፋቸው እንደሸጎጡ እናቶቻቸው
እቅፍ ውስጥ ለዘላለም አሽለቡ።
ጐንደር ጉልበቷ ዛለ።
“ግዝየ ምንድነው?”
1748 ዓ.ም ለምንትዋብ ሆነ ለሃገሪቱ ጥሩ ዓመት አልሆን አለ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በጽኑ ታመመ። እናቴ ትጨነቃለች ብሎ
መታመሙን ደበቀ። ለሀያ አምስት ዓመታት ከእናቱ ጋር በስምምነት፣
በምክክርና በሰላም የገዛው ዳግማዊ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሐሙስ ሰኔ 21 ቀን ዐረፈ። የሕመሙ መንስኤ ባይታወቅም፣ የግራዝማች ኢያሱ እኅት የወንድሟን ደም ለመበቀል መርዝ አብልታው ነው የሚል ወሬ
ጐንደር ውስጥ ተዛመተ፡፡
አሳዛኙ ዜና ለምንትዋብ ደረሳት። ስትበር ልጂጋ ሄደች።
የምትሳሳለት ልጇ በሞት ተለይቷታል። ጉልበቷ ከዳት፤ መቀነቷን ፈታች። ጮኸች። አበደች። “ወዮልኝ ልጄ! ወዮልኝ ውዱ ልቼ! የዐይኖቼ ብርሃን! የልቤ ደስታ! ወዮልኝ ልጄ” እያለች ደረቷን ደቃች፣እየወደቀች ተነሳች፣ ፀጉሯን ነጨች፤ ፊቷን ቧጠጠች።
“የላስታን ዓቀባት ያለፈረስ ያለበቅሎ የወጣህ፣ እንዴት ታሰረ
እግርህ። አገር አንድ ለማረግ እንዳልጣርኸው፣ ጫካ ገብተህ አድነህ እንዳልመጣህ፣ ኸነብር ኻንበሳ ጋር ተጋፍጠህ እንዳላሸነፍህ፣ አሁን ማን እግርህን በገመድ አሰረህ?” እያለች አነባች።
ራሷን እስከመሳት ደረሰች።
“ያ እንደ አንበሳ ሚያስገመግመው ድምፅህ የት ጠፋ? ምን ነበር
እመምህ? መታመመህን ያልነገርኸኝ ምን ሁነህ ነው? ያላንተ ማን አለኝ? የአባትህ ዐደራ ነህ። አንተ ለኔ አባቴ፣ እናቴ፣ እህቴ፣ ወንድሜ፣ ጋሻ መከታዬ፣ ክብሬ፣ ሁሉ ነገሬ ነህ። አሁን ምን ይበጀኛል ልዤ? ኸንግድህ እንዴት ልኖር ነው? እንድህ አልጋ ላይ ተኝተህ ኸማይህ ሞቶ መቀበር ይሻለኝ ነበረ” እያለች ጮኸች።
ወዳጅ፣ ዘመድ፣ መኳንንትና ሌሎችም ለመያዝ አቃታቸው።
“ጠንካራው ማንነትሽ የት ኸደ? እርጋታሽ... አስተዋይነትሽ የት ኸደ? አሁንም ይች አገር ባንቺ ዠርባ ላይ ናት። እንምከር... ሁሉንም ነገር በቅጡ እናርገው” ሲሉ ተማጸኗት።
እሷ ግን መጽናናት አልሆነላትም።
“ማነው እንዳንተ ኸንጉሥ የተገኘ ዠግና ወንድ ልዥ፣ ለጠላቶቹ
ማይመለስ፣ ክንዱ ማይዝል? እንዳንተ ይቅር ባይ፣ ማነው እንዳንተ በሃይማኖቱ ጽኑ? ለድኻ ሚራራ፣ ሚዘክር፣ ማነው? እንዳተ የድኻውን ሮሮ ሰሚ፣ ማነው እንዳንተ ፍርድ ጎደለ፣ ደኻ ተበደለ ብሎ ውነት ፈራጅ? ማነው እንዳንተ አገር ወዳጅ? እንዳተ የናቱን ምክር ሰሚ፣ ማነው? እንዳንተ ታላቆቹን ኣክባሪ፣ ማነው? እንዳንተ ሸጋ ማነው?
እንዳንተ ጥርሰ መልካም፣ እንዳንተ ዕንቁ፣ እንዳንተ ወርቅ ማነው?
አሁን ምን ላርግ? የት ልኸድ? የት ልግባ? ቀድሞ በሕይወትህ
አስደስትኸኝ፣ አሁን በሞትህ አነደድኸኝ” እያለች ዋይታዋ ማባሪያ ኣጣ።
በአጎቷ በደጅአዝማች እሸቴ ራስቢትወደድ ወልደልዑልን
አስጠራች። ወልደልዑል ሲሰማ ሲሮጥ መጣ፤ አበደ፤ ጨርቁን ጣለ።እንደ እሱ የኢያሱን መሞት ያልሰሙ መኳንንት መጉረፍ ሲጀምሩ፣ እንደገና ዋይታና ሰቆቃ ሆነ። ጩኸትና ዋይታ ከዳር እዳር አስተጋባ።
ጩኸቱና ዋይታው ወህኒ አምባ ከመድረሱ ቀደም ብሎ እልፍኝ
አስከልካዮች የብርሃን ሰገድ ኢያሱ አስከሬን ያለበትን ቤተመንግሥት ቆለፉ። ወልደልዑል በአስቸኳይ መደረግ ወዳለበት ነገር ትኩረቱን
አደረገ ምንትዋብን፣ “እቴ ብርሃን ሞገሳ ሆይ፣ ብርሃን ሰገድ
ልዥሽ በሕይወት ሳለ ምን ነግሮሽ ነበር? መንበረ መንግሥቱን ማን
እንደሚወርስ አልነገረሽም? ኸሦስቱ ልዦቹ ከአቤቶ አፅቁ፣ ከአቤቶ ኃይሉና ከአቤቶ ዋዩ መኻል የትኛው ይንገሥ አለ? የነገረሽ ኻለ እባክሽ ንገሪን” ሲል ወተወታት።
“ኸመቤት ውቢት የተወለደው አቤቶ ዋዩ በእኔ መንበረ መንግሥት ይቀመጥ። ዮዳኤ የሰባት ዓመቱን ኢዮአስን እንዳነገሠው እናንተም
ልጄን ኢዮአስን አንግሡት፤ እኔንም አባቴን በካፋንም ሊተካ ይችላል።
ምወደው እሱን ነው” ብሏል፣ አለቻቸው ሲቃ እየተናነቃት።
ወልደልዑል፣ የቅርብ ዘመዶችና የቅርብ መኳንንት በር ዘግተውና
በነፍጥ አስጠብቀው መከሩ። አቤቶ ዋዩ ወይንም ኢዮአስ ገና የሰባት ዓመት ልጅ ነበርና፣ “እቴጌ በነበረችበት ሥልጣን ትቀጥል” ብለው ወሰኑ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ከንስሐ ስትወጣ መቅሰፍት ተከተላት። እሷና ኢያሱ በነገሡ በአስራ ስድስተኛ ዓመታቸው ላይ አንድ ጠዋት ምንትዋብ ወደ ጸሎት ቤት ልትሄድ ስትዘጋጅ፣ አንደኛዋ ደንገጡሯ መጥታ፣ “ኧረ እቴጌ ሰማይ ምድሩ ዕርድ መስሏል” አለቻት፣ ቢጫ ስለለበሰው ሰማይና መሬት።
“እንዴት?”
“እንዲህ ዕርድ ሲመስል በነገታው አንበጣ ይወራል አሉ። ደሞም
ንፋስ እየነፈሰ ነው፣ ሰማዩም ደመና አዝሏል። ሁለቱም ነገሩን
ያባብሱታል።”
ፈጠን ብላ ወደ መስኮቱ ሄደች ምንትዋብ። እውነትም የጐንደር
ሰማይ ቢጫ ሆኗል። አፏን በእጇ ይዛ፣ “ምን ጉድ ነው? ምን ይሻላል?” አለች።
“እግዚኦ ማለት ነው እንጂ ሌላ ምን አለ?” አለች፣ ደንገጡሯ።
ኢያሱ መቸም ይሰማል... ይነግሩታል ኣለች ምንትዋብ፣ ለራሷ።
ካህናቱ በፍጥነት ጸሎት እንዲይዙ መልዕክት ላከችባቸው። ጸሎት
ቤቷ ለመሄድ ወጥታ ተመልሳ እልፍኟ ተቀመጠች። ሰማይና ምድሩ እንደዛ ሆኖ ስታየው አስፈራት።
በማግሥቱ የአንበጣ መንጋ ሰማዩን አለበሰው። የአንድ ቀን ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀናት በመቆየቱ ቤተመንግሥትም ጐንደርም ተጨነቁ፤ተጠበቡ። ሕዝቡ፣ “እግዚኦ” አለ። ታላቅ መቅሰፍት እንደመጣ አመነ።
ምሽት ላይ ሳይቀር አንበጦች ሰማዩን አንለቅ አሉ። ከባድ ዝናብና
ንፋስ ወረራውን አባባሱት።
ውሎ አድሮም ሰብል ተበላሽ። እየቆየ ሲሄድ ጐንደር ትልቅ ችግር
ላይ ስትወድቅ፣ ሕዝቧንና እንስሳዋን ረሐብ አጠወለገው፤ በሽታ አጣደፈው። ቀናትና ወራት እያለፉ ሲመጡ ቀባሪ እስኪጠፋ ሙታን በየወደቁበት ቀሩ። የተረፉት ከነገሥታቱ ጀምሮ በኃይለኛ ጉንፋን ተያዙ። እንዲህ እያለ ሁለት ዓመት አለፈ።
ሰዉ ካደረሰበት ጉዳት ገና ሳያገግም፣ ተምች በመመለሱ ችግር ብቻ ሳይሆን፣ ከቀድሞው የበለጠ ረሐብ ገባ።
ጌታችን ወርዶ ከባሕር፣
ኣዳምን ዋና ሊያስተምር፣
አፋፍ ላይ ሁነን ብናየው፣
እያጣ አለቀ ሰው።
ተብሎ እንደተገጠመው ሁሉ ጐንደርን ጨምሮ በደጋም በቆላም ሰው አለቀ። ከቤተመንግሥት የተቻለውን ያህል የእህል እርዳታ ቢደረግ እያደር ዐቅም አነሰ። የቻለ ጐንደርና አካባቢዋን ጥሎ ተሰደደ ::መሬቱን፣ ንብረቱንና ደብሩን ጥሎ መሄድ ያልሆነለት ለረሐብና ለበሽታ ተጋለጠ።
ጐንደሬዎች የሕይወት ምልክቱ ከፊታቸው ላይ ጠፍቶ ባዶው ላይ
አፈጠጡ። ከንፈራቸው ሐሩርና ውርጭ የመታው ይመስል ከስሞ፣
ቆዳቸው ተሰነጣጥቆ፣ የአንገታቸው ቆዳ ተንጠልጥሎ፣ የጉንጫቸው አጥንት አፈንግጦ፣ የሰለሉ እጆችና እግሮቻቸውን ማንሳት ተስኗቸው በረሐብ፣ በጥምና በበሽታ ተንጠራወዙ።
መከራ በሰዎች ገጽታ ላይ ግዘፍ ነሥቶ ታየ።
ለእናት፣ ለአባትና ለልጅ ቀባሪ የሚሆን ዐቅም ጠፍቶ ጐንደሬዎች
ዐይናቸው ቦዞ፣ እንባቸው ደርቆ፣ እጅና እግራቸው ዝሎ ተቀመጡ።
ትናንት ስቀው፣ ወደው፣ ጠልተው ከቶውንም በልተው የማያውቁ
መሰሉ። ዛሬ ተስፋቸውን ተነጥቀው ከሞት ጋር ተፋጠጡ። ነገ የእነሱ እንዳልሆነች አውቀው እጃቸውን ለሞት ሰጡ።
ሞት፣ ያ የሰው ልጅ የቁም ቅዠት አላስደነግጥ አለ። እንደተራ
ነገር ተቆጠረ። ጐንደሬዎች የሚዘክራቸው መላዕክትና ቅዱሳን ሁሉ ወዴት እንደሄዱ ጠየቁ። የእግዚአብሔርንም መኖሪያ አጠያየቁ። እንደ ዳዊት፣ “ጆሮን የፈጠረ አይሰማምን? ዐይንን የፈጠረ አያይምን?” ብለው
አቤቱታ አስገቡ። ሕጻናት ጡት አፋቸው እንደሸጎጡ እናቶቻቸው
እቅፍ ውስጥ ለዘላለም አሽለቡ።
ጐንደር ጉልበቷ ዛለ።
“ግዝየ ምንድነው?”
1748 ዓ.ም ለምንትዋብ ሆነ ለሃገሪቱ ጥሩ ዓመት አልሆን አለ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ በጽኑ ታመመ። እናቴ ትጨነቃለች ብሎ
መታመሙን ደበቀ። ለሀያ አምስት ዓመታት ከእናቱ ጋር በስምምነት፣
በምክክርና በሰላም የገዛው ዳግማዊ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሐሙስ ሰኔ 21 ቀን ዐረፈ። የሕመሙ መንስኤ ባይታወቅም፣ የግራዝማች ኢያሱ እኅት የወንድሟን ደም ለመበቀል መርዝ አብልታው ነው የሚል ወሬ
ጐንደር ውስጥ ተዛመተ፡፡
አሳዛኙ ዜና ለምንትዋብ ደረሳት። ስትበር ልጂጋ ሄደች።
የምትሳሳለት ልጇ በሞት ተለይቷታል። ጉልበቷ ከዳት፤ መቀነቷን ፈታች። ጮኸች። አበደች። “ወዮልኝ ልጄ! ወዮልኝ ውዱ ልቼ! የዐይኖቼ ብርሃን! የልቤ ደስታ! ወዮልኝ ልጄ” እያለች ደረቷን ደቃች፣እየወደቀች ተነሳች፣ ፀጉሯን ነጨች፤ ፊቷን ቧጠጠች።
“የላስታን ዓቀባት ያለፈረስ ያለበቅሎ የወጣህ፣ እንዴት ታሰረ
እግርህ። አገር አንድ ለማረግ እንዳልጣርኸው፣ ጫካ ገብተህ አድነህ እንዳልመጣህ፣ ኸነብር ኻንበሳ ጋር ተጋፍጠህ እንዳላሸነፍህ፣ አሁን ማን እግርህን በገመድ አሰረህ?” እያለች አነባች።
ራሷን እስከመሳት ደረሰች።
“ያ እንደ አንበሳ ሚያስገመግመው ድምፅህ የት ጠፋ? ምን ነበር
እመምህ? መታመመህን ያልነገርኸኝ ምን ሁነህ ነው? ያላንተ ማን አለኝ? የአባትህ ዐደራ ነህ። አንተ ለኔ አባቴ፣ እናቴ፣ እህቴ፣ ወንድሜ፣ ጋሻ መከታዬ፣ ክብሬ፣ ሁሉ ነገሬ ነህ። አሁን ምን ይበጀኛል ልዤ? ኸንግድህ እንዴት ልኖር ነው? እንድህ አልጋ ላይ ተኝተህ ኸማይህ ሞቶ መቀበር ይሻለኝ ነበረ” እያለች ጮኸች።
ወዳጅ፣ ዘመድ፣ መኳንንትና ሌሎችም ለመያዝ አቃታቸው።
“ጠንካራው ማንነትሽ የት ኸደ? እርጋታሽ... አስተዋይነትሽ የት ኸደ? አሁንም ይች አገር ባንቺ ዠርባ ላይ ናት። እንምከር... ሁሉንም ነገር በቅጡ እናርገው” ሲሉ ተማጸኗት።
እሷ ግን መጽናናት አልሆነላትም።
“ማነው እንዳንተ ኸንጉሥ የተገኘ ዠግና ወንድ ልዥ፣ ለጠላቶቹ
ማይመለስ፣ ክንዱ ማይዝል? እንዳንተ ይቅር ባይ፣ ማነው እንዳንተ በሃይማኖቱ ጽኑ? ለድኻ ሚራራ፣ ሚዘክር፣ ማነው? እንዳተ የድኻውን ሮሮ ሰሚ፣ ማነው እንዳንተ ፍርድ ጎደለ፣ ደኻ ተበደለ ብሎ ውነት ፈራጅ? ማነው እንዳንተ አገር ወዳጅ? እንዳተ የናቱን ምክር ሰሚ፣ ማነው? እንዳንተ ታላቆቹን ኣክባሪ፣ ማነው? እንዳንተ ሸጋ ማነው?
እንዳንተ ጥርሰ መልካም፣ እንዳንተ ዕንቁ፣ እንዳንተ ወርቅ ማነው?
አሁን ምን ላርግ? የት ልኸድ? የት ልግባ? ቀድሞ በሕይወትህ
አስደስትኸኝ፣ አሁን በሞትህ አነደድኸኝ” እያለች ዋይታዋ ማባሪያ ኣጣ።
በአጎቷ በደጅአዝማች እሸቴ ራስቢትወደድ ወልደልዑልን
አስጠራች። ወልደልዑል ሲሰማ ሲሮጥ መጣ፤ አበደ፤ ጨርቁን ጣለ።እንደ እሱ የኢያሱን መሞት ያልሰሙ መኳንንት መጉረፍ ሲጀምሩ፣ እንደገና ዋይታና ሰቆቃ ሆነ። ጩኸትና ዋይታ ከዳር እዳር አስተጋባ።
ጩኸቱና ዋይታው ወህኒ አምባ ከመድረሱ ቀደም ብሎ እልፍኝ
አስከልካዮች የብርሃን ሰገድ ኢያሱ አስከሬን ያለበትን ቤተመንግሥት ቆለፉ። ወልደልዑል በአስቸኳይ መደረግ ወዳለበት ነገር ትኩረቱን
አደረገ ምንትዋብን፣ “እቴ ብርሃን ሞገሳ ሆይ፣ ብርሃን ሰገድ
ልዥሽ በሕይወት ሳለ ምን ነግሮሽ ነበር? መንበረ መንግሥቱን ማን
እንደሚወርስ አልነገረሽም? ኸሦስቱ ልዦቹ ከአቤቶ አፅቁ፣ ከአቤቶ ኃይሉና ከአቤቶ ዋዩ መኻል የትኛው ይንገሥ አለ? የነገረሽ ኻለ እባክሽ ንገሪን” ሲል ወተወታት።
“ኸመቤት ውቢት የተወለደው አቤቶ ዋዩ በእኔ መንበረ መንግሥት ይቀመጥ። ዮዳኤ የሰባት ዓመቱን ኢዮአስን እንዳነገሠው እናንተም
ልጄን ኢዮአስን አንግሡት፤ እኔንም አባቴን በካፋንም ሊተካ ይችላል።
ምወደው እሱን ነው” ብሏል፣ አለቻቸው ሲቃ እየተናነቃት።
ወልደልዑል፣ የቅርብ ዘመዶችና የቅርብ መኳንንት በር ዘግተውና
በነፍጥ አስጠብቀው መከሩ። አቤቶ ዋዩ ወይንም ኢዮአስ ገና የሰባት ዓመት ልጅ ነበርና፣ “እቴጌ በነበረችበት ሥልጣን ትቀጥል” ብለው ወሰኑ።
👍14👏1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....“ግዝየ እኛ ነን።”
ጥላዬ፣ በወርቅ ያሸበረቀችው ቁስቋም ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ሲገባ በቤተክርስቲያኗ ውበት ተማረከ። በአጥሩ ግንብ ማማር ተደነቀ።ፀሐይዋ አለዚያን ቀን እንደዚያ አብርታ የማታውቅ መስላ ታየችው።ቆም ብሎ ሁሉን በዓይኑ ቃኘ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከሞተ በኋላ፣ ምንትዋብን የማግኘት ፍላጎቱ
ቢበረታም አስራ ዐራት ዓመት ሙሉ ቆርጦ አለመነሳቱ ኅሊናውን
ሲቆጠቁጠው ቆይቶ፣ የኢዮአስን ሞትና የመንግሥቱን ማብቃት ሲሰማ አላስችል ብሎት ወደ ጐንደር አቀና።
ከአብርሃም ቤት ወጥቶ ቁልቁል ሲወርድ፣ የተጫጫነው ትካዜ፣ ገና ከደብረ ወርቅ ሲነሳ ምንትዋብ ላይ የደረሰው ድርብ ሐዘን፣ የጐንደር መበጥበጥ፣ የሃገሩ መረበሽ የልብ ስብራት የፈጠረበት መሆኑ ቀርቶ ዛሬ ቁስቋም ግቢ ውስጥ ሲቆም፣ ድንገት ሰላምና መረጋጋት በማግኘቱ ያችን ሰዐት ለዘላለም ለማቆየት የፈለገ ይመስል እዚያው ያለበት ቦታ
ቆሞ ቀረ።
ውስጡ የተቀጣጠለው የተስፋ ስሜት ያቺ ደማቅ ፀሐይ ከረጨችው ብርሃን ጋር ተዋሕዶ ልቡን አሞቀው። ለጊዜው እዚያ ቦታ ላይ ለምን እንደተገኘ ረስቶ፣ ሄዶ መሳለም ብሎም ጸሎት ማድረስ እንዳለበት ዘንግቶ ከቆመበት አልንቀሳቀስ አለ። ቁስቋምን በምናቡ ብራና ላይ
ሣላት። ቀደም ብሎ ጐንደር እንዲመጣ በሮብዓም ግብዣ ሲቀርብለት አለመቀበሉ የሚያየው ውበትና ታሪክ ተካፋይ ሳያደርገው በመቅረቱ ተቆጨ። አንዲት መነኩሴ እጅ ሲነሱት ደንገጥ ብሎ ሰላምታ ሰጣቸው።
ምን ያህል ጊዜ እዚያ እንደቆመ ባያውቅም ወደ ቤተክርስቲያኗ በዝግታ አመራ። በወንዶቹ መግቢያ በኩል ሄዶ በሩን ተሳለመ። ቆም ብሎም
ዳዊቱን ከማኅደሩ አውጥቶ ደገመ።
ሲጨርስ፣ ዙርያውን ተመለከተ። ወደ ቤተመንግሥት የሚመራው
ሰው በዓይኑ ፈለግ ፈለግ አደረገ። ወደ መጣበት ሲመለስ፣ አንድ ቄስ
ከግቢ ሊወጡ ሲሉ አያቸውና “አባቴ!” ብሎ አስቆማቸው። እንዲባርኩት ከተጠጋቸው በኋላ፣ ወደ “እቴጌ ቤተመንግሥት በየት ነው ምሄድ?” ሲል ጠየቃቸው።
ቄሱም፣ “በዝያ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ሲኸዱ ዘበኞቹን ያያሉ።
እነሱ ያሳይዎታል” ብለውት ተሰናበቱት።
ተመልሶ ወደ ቤተክርስቲያኒቱ ወንዶች መግቢያ አመራ። በስተጀርባ በኩል ቁልቁል ሲወርድ፣ ቄሱ እንዳሉት በግንብ የታጠረው በር ላይ ዘበኞች ቆመዋል። ትኩር ብለው ያዩታል። ራቅ ብሎ እጅ ነሳና፣ “እቴጌ
ዘንድ ጉዳይ ነበረኝ። ስሜ ሥሙር ነው። ኸነማይ ነው የመጣሁት።
የእቴጌ ዘመድ ነኝ።” ብሎ የያዘውን የተጠቀለለ ዕቃ አሳያቸው።
ዘበኞቹ፣ ጉዳዩ ምን እንደሆነ ደግመው ደጋግመው ከጠየቁት በኋላ፣እንዲጠብቅ ነግረውት አንደኛው ወደ ውስጥ ገባ። ጥቂት ቆይቶ አንድ ያደገደገ አስተናጋጅ መጥቶ ማን እንደሆነና ጉዳዩ ምን እንደሆነ አጥብቆ ከጠየቀው በኋላ ሄደ። ጥላዬ እንደገና ዘለግ ላለ ተጨማሪ ጊዜ ከጠበቀ በኋላ፣ አስተናጋጁ ተመልሶ መጥቶ እንዲከተለው በእጁ
ምልክት ሰጠው።
ግቢው ውስጥ ሲገባ፣ የምንትዋብ ቤተመንግሥት ከፊት ለፊቱ ገዝፎ ታየው። በስተቀኙ ያለው የጸሎት ቤቷን እያደነቀ ሲሄድ ግቢው ውስጥ ያለው የሰው ብዛትና ጫጫታ ገረመው። ሕፃናት ከወዲያ ወዲህ ይራወጣሉ። “ኸነዝኸህ ውስጥ የልዥ ልዧቿ አሉበት መቸም”
ብሎ ወደፊት ሲመለከት ወይዛዝርትና ባለሟሎች ከወዲያ ወዲህ ይዘዋወራሉ። አስተናጋጁ በዝምታ ሲመራው ድንገት ግዙፍ የሆነ ግንብ ሲያይ ዝናውን የሰማው “ሽናዋ” የግብር አዳራሽ መሆኑ ገባው።የግንቡ ማማር ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዓይኑን አጭበረበረው።ምንትዋብን ራሷን እንደዛ ገዝፋ ያያት መሰለው።
ስለ ምንትዋብ ሲያስብ፣ ምን እንደሚጠብቅ ማወቅ አልቻለም።
ልጄ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሞቶ፣ ቤተመንግሥት ሁለት ተከፍሎ ብሎም ፍርክስክሱ ወጥቶ፣ ወጣቱ ንጉሠ ነገሥት አድያም ሰገድ ኢዮአስ በሻሽ ታንቆ ተገድሎ፣ ሬሳው ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ፣ መሣፍንት በየበኩላቸው
ተቆራቁሰው፣ ሃገር ተተራምሶ፣ ወንድሟ ወልደልዑልና ዘመዶቿ አንድ በአንድ ሞተው፣ እሷ ቤተመንግሥቱን ጥላ ወጥታ ምን ልትመስል እንደምትችል መገመት ተሳነው። ቁስቋም ግቢ ውስጥ ሲገባ ተሰምቶት የነበረው የመንፈስ መነቃቃት ከውስጡ ሊተን ቃጣው።
አስተናጋጁ፣ በሽናዋ አዳራሽ በስተቀኝ በኩል ወዳለው እንቁላል
ግንብ ወደሚወስደው ደረጃ ሲወጣ ተከትሎት ወጣ። ቁና ቁና ተነፈሰ።ጉልበቱ ላለበት። ዕድሜው እንደገፋ ቢያውቅም አሁን በቅጽበት ጨምሮ የሸመገለ መሰለው። ደረጃውን ሲጨርሱ፣ ላብ አሰመጠው።በፍጥነት ግንባሩን ያራሰውን ላብ በኩታው ተም ተም አደረገው። እጁ
ውስጥ ሊንቆረቆር የሚታገለውን ላብ እጀ ጠባቡ ላይ ጠራረገው። በርላይ ሲደርሱ ቆም ብሎ ኩታውን አስተካከለ።
ግራና ቀኝ ያደገደጉ አስተናጋጆች ቆመዋል። አስተናጋጁ እርሱን
ለእነሱ አስረክቦ ወደኋላ ሲቀር፣ አንደኛው እልፍኝ አስከልካይ እጅ
ነስቶ “ይግቡ” አለና ቀደም ብሎ ገብቶ እጅ ነስቶ፣ “እቴጌ እንግዳው መጥተዋል” ብሎ አስቀደመው
ጥላዬ፣ ልቡ ከታች ምላሱ ካላይ ጉሮሮውን የዘጉበት መሰለው።
ምንትዋብ፣ ቀይ ከፋይ የለበሰ ሰፊ ወንበር ላይ ተቀምጣለች።
የለበሰችው ረጅምና ባለቀይ ጥበብ ቀሚስ ላይ የደረበችው በወርቅ ያጌጠው ሰማያዊ ካባ ልዩ ድምቀት ሰጥቷታል። ሹሩባዋ ላይ ሸብ ያደረገችው ነጭ ሐር ሻሽ ግርማ ሞገስ አክሎላቷል።
ጥላዬ፣ ልቡ ቷ አለበት፤ ሰውነቱ ራደ። ግርማ ሞገሷ አስፈራው።
ለጥ ብሎ እጅ ነሣ። ያ በር ላይ ሲደርስ ሊያጥለቀልቀው የቃጣው
ላብ ፊቱ ላይ ክልብስ አለበት።
“ይቀመጡ” ብላ፣ ፊት ለፊቷ ያለ ወንበር በእጇ አሳየችው።
በእጁ ግንባሩን አሻሽና በጨርቅ የተጠቀለለውን ብራና ከብብቱ
ስር አውጥቶ፣ የተሸፈነበትን ጨርቅ ከላዩ ላይ አንስቶ እንደገና ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ፣ ሲሰጣት ምንትዋብ ተቀበለችው። ዕንጨት ላይ የተወጠረውን ብራና ስታየው ከዓመታት በፊት መነኩሴው ይዘውት መጥተው የነበረው ዓይነት የራሷ ምስል ነው።
“እርስዎን ደሞ ማን ላከዎት?” አለችው።
“ማነም አላከኝ። ዛሬስ ራሴ መጣሁ።”
“ሥሙር ማለት እርስዎ ነዎት?”
“እርስዎ አያስታውሱኝም። ግዝየውም ርቋል። የባላምባራስ ሁነኝ ልዥ ... ጥላዬ ነኝ።”
“ባላምባራስ ሁነኝ የቋራው ... የሳቸው ልዥ ... ጥላዬ?” ብላ የሷ
ያልመሰላት ድምፅ ከውስጧ ሲወጣ ተሰማት።
“አዎ... የቋራው ... ጥላዬ።”
ምንትዋብ ደነገጠች፤ ምላሷ ተቆለፈ። ከጥቂት ዝምታ በኋላ
እንደምንም ብላ፣ “ኧረ... በቁስቋሟ ተቀመጥ እንጂ!” አለችው፣ ወንበር እያመለከተችው።
ተቀመጠ።
ሁለቱም በዝምታ ተያዩ።
“ለካንስ አንተ ኑረኻል ካንዴም ሁለቴ ምስል ስትልክ የነበርኸው።
ለመሆኑ እስተዛሬ የት ነበርህ?”
ጥላዬ ፈገግ ብሎ ዝም አለ። ከመምጣቱ በፊት ሊላት በሐሳቡ
ያወጣው ያወረደው፣ ያለመውና የተመኘው ሁሉ ከጭንቅላቱ ብን
ብሎ ጠፍቷል። የቀረው ዝምታ ብቻ ብዙ ሐሳቦችን፣ በርካታ
ትዝታዎችንና ስሜቶችን የያዘ ከንግግር የላቀ ዝምታ። ለዚህ ቀን
ምን ዓይነት ቃላት ይበቁ ነበር? በዚያ ሁሉ የሐሳብ ውዥንብር ውስጥ አንድ ነገር ከአእምሮው አልወጣ አለ ንግሥታዊ ግርማ ሞገሷ።አፍዝ አደንግዝ የያዘው ይመስል አፉ ተሳሰረ። ስትናገር ደንገጥ ብሎ መስማት ጀመረ።
“ዛዲያ እስተዛሬ እንደዝኽ መምጣት እየቻልህ ስለምን ይኸን ያህል ግዝየ ቆየህ? እኔኮ ኸቋራ ኸወጣሁ ዠምሮ የት እንደደረስህም አላውቅም
ነበረ። ቤተመንግሥት እኮ እንዲህ ኸዘመድ እንደልብ ሚያገናኝ ቦታ
ማዶል ። እንደዝህ ስጎዳ ስለምን አልጠየቅኸኝም?”
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....“ግዝየ እኛ ነን።”
ጥላዬ፣ በወርቅ ያሸበረቀችው ቁስቋም ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ሲገባ በቤተክርስቲያኗ ውበት ተማረከ። በአጥሩ ግንብ ማማር ተደነቀ።ፀሐይዋ አለዚያን ቀን እንደዚያ አብርታ የማታውቅ መስላ ታየችው።ቆም ብሎ ሁሉን በዓይኑ ቃኘ።
ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከሞተ በኋላ፣ ምንትዋብን የማግኘት ፍላጎቱ
ቢበረታም አስራ ዐራት ዓመት ሙሉ ቆርጦ አለመነሳቱ ኅሊናውን
ሲቆጠቁጠው ቆይቶ፣ የኢዮአስን ሞትና የመንግሥቱን ማብቃት ሲሰማ አላስችል ብሎት ወደ ጐንደር አቀና።
ከአብርሃም ቤት ወጥቶ ቁልቁል ሲወርድ፣ የተጫጫነው ትካዜ፣ ገና ከደብረ ወርቅ ሲነሳ ምንትዋብ ላይ የደረሰው ድርብ ሐዘን፣ የጐንደር መበጥበጥ፣ የሃገሩ መረበሽ የልብ ስብራት የፈጠረበት መሆኑ ቀርቶ ዛሬ ቁስቋም ግቢ ውስጥ ሲቆም፣ ድንገት ሰላምና መረጋጋት በማግኘቱ ያችን ሰዐት ለዘላለም ለማቆየት የፈለገ ይመስል እዚያው ያለበት ቦታ
ቆሞ ቀረ።
ውስጡ የተቀጣጠለው የተስፋ ስሜት ያቺ ደማቅ ፀሐይ ከረጨችው ብርሃን ጋር ተዋሕዶ ልቡን አሞቀው። ለጊዜው እዚያ ቦታ ላይ ለምን እንደተገኘ ረስቶ፣ ሄዶ መሳለም ብሎም ጸሎት ማድረስ እንዳለበት ዘንግቶ ከቆመበት አልንቀሳቀስ አለ። ቁስቋምን በምናቡ ብራና ላይ
ሣላት። ቀደም ብሎ ጐንደር እንዲመጣ በሮብዓም ግብዣ ሲቀርብለት አለመቀበሉ የሚያየው ውበትና ታሪክ ተካፋይ ሳያደርገው በመቅረቱ ተቆጨ። አንዲት መነኩሴ እጅ ሲነሱት ደንገጥ ብሎ ሰላምታ ሰጣቸው።
ምን ያህል ጊዜ እዚያ እንደቆመ ባያውቅም ወደ ቤተክርስቲያኗ በዝግታ አመራ። በወንዶቹ መግቢያ በኩል ሄዶ በሩን ተሳለመ። ቆም ብሎም
ዳዊቱን ከማኅደሩ አውጥቶ ደገመ።
ሲጨርስ፣ ዙርያውን ተመለከተ። ወደ ቤተመንግሥት የሚመራው
ሰው በዓይኑ ፈለግ ፈለግ አደረገ። ወደ መጣበት ሲመለስ፣ አንድ ቄስ
ከግቢ ሊወጡ ሲሉ አያቸውና “አባቴ!” ብሎ አስቆማቸው። እንዲባርኩት ከተጠጋቸው በኋላ፣ ወደ “እቴጌ ቤተመንግሥት በየት ነው ምሄድ?” ሲል ጠየቃቸው።
ቄሱም፣ “በዝያ በወንዶቹ መግቢያ በኩል ሲኸዱ ዘበኞቹን ያያሉ።
እነሱ ያሳይዎታል” ብለውት ተሰናበቱት።
ተመልሶ ወደ ቤተክርስቲያኒቱ ወንዶች መግቢያ አመራ። በስተጀርባ በኩል ቁልቁል ሲወርድ፣ ቄሱ እንዳሉት በግንብ የታጠረው በር ላይ ዘበኞች ቆመዋል። ትኩር ብለው ያዩታል። ራቅ ብሎ እጅ ነሳና፣ “እቴጌ
ዘንድ ጉዳይ ነበረኝ። ስሜ ሥሙር ነው። ኸነማይ ነው የመጣሁት።
የእቴጌ ዘመድ ነኝ።” ብሎ የያዘውን የተጠቀለለ ዕቃ አሳያቸው።
ዘበኞቹ፣ ጉዳዩ ምን እንደሆነ ደግመው ደጋግመው ከጠየቁት በኋላ፣እንዲጠብቅ ነግረውት አንደኛው ወደ ውስጥ ገባ። ጥቂት ቆይቶ አንድ ያደገደገ አስተናጋጅ መጥቶ ማን እንደሆነና ጉዳዩ ምን እንደሆነ አጥብቆ ከጠየቀው በኋላ ሄደ። ጥላዬ እንደገና ዘለግ ላለ ተጨማሪ ጊዜ ከጠበቀ በኋላ፣ አስተናጋጁ ተመልሶ መጥቶ እንዲከተለው በእጁ
ምልክት ሰጠው።
ግቢው ውስጥ ሲገባ፣ የምንትዋብ ቤተመንግሥት ከፊት ለፊቱ ገዝፎ ታየው። በስተቀኙ ያለው የጸሎት ቤቷን እያደነቀ ሲሄድ ግቢው ውስጥ ያለው የሰው ብዛትና ጫጫታ ገረመው። ሕፃናት ከወዲያ ወዲህ ይራወጣሉ። “ኸነዝኸህ ውስጥ የልዥ ልዧቿ አሉበት መቸም”
ብሎ ወደፊት ሲመለከት ወይዛዝርትና ባለሟሎች ከወዲያ ወዲህ ይዘዋወራሉ። አስተናጋጁ በዝምታ ሲመራው ድንገት ግዙፍ የሆነ ግንብ ሲያይ ዝናውን የሰማው “ሽናዋ” የግብር አዳራሽ መሆኑ ገባው።የግንቡ ማማር ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዓይኑን አጭበረበረው።ምንትዋብን ራሷን እንደዛ ገዝፋ ያያት መሰለው።
ስለ ምንትዋብ ሲያስብ፣ ምን እንደሚጠብቅ ማወቅ አልቻለም።
ልጄ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ሞቶ፣ ቤተመንግሥት ሁለት ተከፍሎ ብሎም ፍርክስክሱ ወጥቶ፣ ወጣቱ ንጉሠ ነገሥት አድያም ሰገድ ኢዮአስ በሻሽ ታንቆ ተገድሎ፣ ሬሳው ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ፣ መሣፍንት በየበኩላቸው
ተቆራቁሰው፣ ሃገር ተተራምሶ፣ ወንድሟ ወልደልዑልና ዘመዶቿ አንድ በአንድ ሞተው፣ እሷ ቤተመንግሥቱን ጥላ ወጥታ ምን ልትመስል እንደምትችል መገመት ተሳነው። ቁስቋም ግቢ ውስጥ ሲገባ ተሰምቶት የነበረው የመንፈስ መነቃቃት ከውስጡ ሊተን ቃጣው።
አስተናጋጁ፣ በሽናዋ አዳራሽ በስተቀኝ በኩል ወዳለው እንቁላል
ግንብ ወደሚወስደው ደረጃ ሲወጣ ተከትሎት ወጣ። ቁና ቁና ተነፈሰ።ጉልበቱ ላለበት። ዕድሜው እንደገፋ ቢያውቅም አሁን በቅጽበት ጨምሮ የሸመገለ መሰለው። ደረጃውን ሲጨርሱ፣ ላብ አሰመጠው።በፍጥነት ግንባሩን ያራሰውን ላብ በኩታው ተም ተም አደረገው። እጁ
ውስጥ ሊንቆረቆር የሚታገለውን ላብ እጀ ጠባቡ ላይ ጠራረገው። በርላይ ሲደርሱ ቆም ብሎ ኩታውን አስተካከለ።
ግራና ቀኝ ያደገደጉ አስተናጋጆች ቆመዋል። አስተናጋጁ እርሱን
ለእነሱ አስረክቦ ወደኋላ ሲቀር፣ አንደኛው እልፍኝ አስከልካይ እጅ
ነስቶ “ይግቡ” አለና ቀደም ብሎ ገብቶ እጅ ነስቶ፣ “እቴጌ እንግዳው መጥተዋል” ብሎ አስቀደመው
ጥላዬ፣ ልቡ ከታች ምላሱ ካላይ ጉሮሮውን የዘጉበት መሰለው።
ምንትዋብ፣ ቀይ ከፋይ የለበሰ ሰፊ ወንበር ላይ ተቀምጣለች።
የለበሰችው ረጅምና ባለቀይ ጥበብ ቀሚስ ላይ የደረበችው በወርቅ ያጌጠው ሰማያዊ ካባ ልዩ ድምቀት ሰጥቷታል። ሹሩባዋ ላይ ሸብ ያደረገችው ነጭ ሐር ሻሽ ግርማ ሞገስ አክሎላቷል።
ጥላዬ፣ ልቡ ቷ አለበት፤ ሰውነቱ ራደ። ግርማ ሞገሷ አስፈራው።
ለጥ ብሎ እጅ ነሣ። ያ በር ላይ ሲደርስ ሊያጥለቀልቀው የቃጣው
ላብ ፊቱ ላይ ክልብስ አለበት።
“ይቀመጡ” ብላ፣ ፊት ለፊቷ ያለ ወንበር በእጇ አሳየችው።
በእጁ ግንባሩን አሻሽና በጨርቅ የተጠቀለለውን ብራና ከብብቱ
ስር አውጥቶ፣ የተሸፈነበትን ጨርቅ ከላዩ ላይ አንስቶ እንደገና ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ፣ ሲሰጣት ምንትዋብ ተቀበለችው። ዕንጨት ላይ የተወጠረውን ብራና ስታየው ከዓመታት በፊት መነኩሴው ይዘውት መጥተው የነበረው ዓይነት የራሷ ምስል ነው።
“እርስዎን ደሞ ማን ላከዎት?” አለችው።
“ማነም አላከኝ። ዛሬስ ራሴ መጣሁ።”
“ሥሙር ማለት እርስዎ ነዎት?”
“እርስዎ አያስታውሱኝም። ግዝየውም ርቋል። የባላምባራስ ሁነኝ ልዥ ... ጥላዬ ነኝ።”
“ባላምባራስ ሁነኝ የቋራው ... የሳቸው ልዥ ... ጥላዬ?” ብላ የሷ
ያልመሰላት ድምፅ ከውስጧ ሲወጣ ተሰማት።
“አዎ... የቋራው ... ጥላዬ።”
ምንትዋብ ደነገጠች፤ ምላሷ ተቆለፈ። ከጥቂት ዝምታ በኋላ
እንደምንም ብላ፣ “ኧረ... በቁስቋሟ ተቀመጥ እንጂ!” አለችው፣ ወንበር እያመለከተችው።
ተቀመጠ።
ሁለቱም በዝምታ ተያዩ።
“ለካንስ አንተ ኑረኻል ካንዴም ሁለቴ ምስል ስትልክ የነበርኸው።
ለመሆኑ እስተዛሬ የት ነበርህ?”
ጥላዬ ፈገግ ብሎ ዝም አለ። ከመምጣቱ በፊት ሊላት በሐሳቡ
ያወጣው ያወረደው፣ ያለመውና የተመኘው ሁሉ ከጭንቅላቱ ብን
ብሎ ጠፍቷል። የቀረው ዝምታ ብቻ ብዙ ሐሳቦችን፣ በርካታ
ትዝታዎችንና ስሜቶችን የያዘ ከንግግር የላቀ ዝምታ። ለዚህ ቀን
ምን ዓይነት ቃላት ይበቁ ነበር? በዚያ ሁሉ የሐሳብ ውዥንብር ውስጥ አንድ ነገር ከአእምሮው አልወጣ አለ ንግሥታዊ ግርማ ሞገሷ።አፍዝ አደንግዝ የያዘው ይመስል አፉ ተሳሰረ። ስትናገር ደንገጥ ብሎ መስማት ጀመረ።
“ዛዲያ እስተዛሬ እንደዝኽ መምጣት እየቻልህ ስለምን ይኸን ያህል ግዝየ ቆየህ? እኔኮ ኸቋራ ኸወጣሁ ዠምሮ የት እንደደረስህም አላውቅም
ነበረ። ቤተመንግሥት እኮ እንዲህ ኸዘመድ እንደልብ ሚያገናኝ ቦታ
ማዶል ። እንደዝህ ስጎዳ ስለምን አልጠየቅኸኝም?”
👍8
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ለዓመታት በርካታ የመንፈስ ድል ስትቀዳጅ ቆይታ ልጇ ከሞተ በኋላ፣ ይኸው ድል ወደ ሽንፈት የተቀየረ በመሰላት ሰዐት እሱን በማግኘቷ ልቧ ተነሳስቶ ኸንግዲህ ሞት እንጂ ሌላ አይለየንም አለች።
አስተናጋጅ ወይን ጠጅ አምጥቶ ቀድቶላቸው ወጣ።
“ጠጣ እስቲ!” አለችው፣ ፈገግ ብላ።
የትካዜው ድባብ ተገፈፈ።
“ለመሆኑ ሥዕል እንዴት ዠመርህ?”
“ቋራ ሁኘ ነው የዠመርሁት” አለና ስለግድግዳው ታሪክ ነገራት።
ከት ብላ ሳቀች። “ሥዕል ትሥል እንደነበር ዛዲያ እንዴት
አላወቅሁም?”
“አባባ ለምሠራው ነገር ቁብ ሰጥተውት አያውቁም ነበር። ወዲያው ያጠፉት ነበረ። ቋራን ትቸ ጐንደር ዘልቄ እመኝ የነበረውን ሥዕል መማር ዠመርሁ። ኋላም ደብረ ወርቅ ማርያም ኸድሁ። መቸም በርስዎና በንጉሥ ኢያሱ ዘመን ሥዕል አደገ። ጐንደር ውስጥ የባሕር ማዶ ሰዎች ኸመጡ ወዲያ ሥዕል ለውጥ ኣምጥቶ ነበረ...” ብሎ ከጠጁ
ተጎነጨ።
“እንዴት?”
“የቀድሞዎቹን ሥዕሎች ያስተዋሉ እንደሆን መለኮታዊ ይዘት
ያላቸውና ታሪክ ተራኪ ነበሩ። ኋላ ግን መለኮታዊ ብቻ ሳይሆን ሥዕል ወደ ሰው ወረደ። ሥጋ ለባሾች... ነገሥታት ሚሣሉበት ዘመን ላይ መጣን። የቀለም አጠቃቀም ሁሉ ለውጥ አመጣ። መቸም የአጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመንም በትምርትም ሆነ በሥዕል ብዙ ለውጥ የመጣበት
ዘመን ነበር። ቁም ጸሐፊው፣ ደብተራው ቁጭ ማለት ያመጣበት ግዝየ ስለነበረ ቁጭ ሲባል ፉክክር፣ ክርክርና አሳብ ለአሳብ መለዋወጥ መጣ።እንዲያም ብሎ አንድምታ ትምርት ተዠመረ። ይኸ አሳብን መግለጽ ወደ ሥዕለም መጣ።”
“እንዴት ያለ ነገር ነገርኸኝ? ሁሉ ሚሆነው በግዝየው ነው መሰለኝ
ብላ ፈገግ አለች።
“አዎ ሁሉ ሚሆነው በግዝየና በቦታ ነው። አለግዝየውና አለቦታው ሚሆን ምን አለ?”
“ግዝየ ምንድነው?”
“ግዝየ እኛ ነን።”
“የግዝየ ነገር ይገርመኛል።”
“የሰው ነገር ይገርመኛል ማለትዎ ነው? ግዝየን ሆነ ቦታን ምንፈጥር
እኛ ሰዎች እኮ ነን። እዝጊሃር ምድርና ሰማይን ፈጠረ። እኛ ደሞ
ግዝየንና ቦታን ፈጠርን። ግዝየ ሆነ ቦታ አለኛ የሉም? ቦታም ግዝየም እኛ ነን። እኛ ጥሩ ስንሆን ግዝየም ጥሩ ይሆናል። እኛ ጥሩ ስንሆን የሰማዩም ደስ ይለዋል፣ ምድርም ለፍጥረታት ሁሉ ምቹ ቦታ
ትሆናለች።”
“አሳብህ ገባኝ። ግዝየ ሳይሆን እኛ ነን ምንገርመው ማለትህ ነው?
እንግዲያማ የሰው ነገር ይገርመኛል።”
“አየ እቴጌ ዝናዎን ሰምቻለሁ። ሊቃውንት ሆኑ ካህናት ያደንቅዎታል።እርስዎ የጠለቀ ዕውቀት... ትምርት ያለዎ... አንደበታምና ታሪክ
አስተካካይ... የሰው ባሕርይ ይግረምዎ?”
“አንተ የሥዕል ንጉሥ፣ የሰማዩንም የምድሩንም ብራና ላይ
ምታስቀምጥ እስቲ ንገረኝ። ሰው ማለት ምን ማለት ነው?”
“እቴጌ ሰው ማለት ምን ማለት እንደሆነ ኻወቅሁማ ፈጣሪን ሆንሁ።እኛ ሰዎች መሆን የነበረብን ሚዛኑ ከፍ አለና እኛ አነስን። መሆን ሚገባንን መሆን አልቻልንም። መቸም ጉድለት አለን ብንል ፈጣሪ ጉድለት ያለው ፈጠረ ማለት ይሆንብናል። ሙሉ ግን ማዶለን።”
“ዛዲያ የተሟላን መሆን ቢያቅተን፣ ኸሚዛኑ ብንጎድል፣ ለመሙላት
አንጥርምን?”
“ቢሆንልንማ እንዲያ ነበር።”
“እኔስ እንዲያው በተለየ አሁን ያለንበትን ሳስብ ክፋትና ደግነት
አብረውን የተወለዱ ናቸው ነው እምል።”
“ስለ ሰው ባሕርይ ተመራምረን ምንደርስበት አይመስለኝም::”
አለ ጥላዬ ከጠጁ አሁንም ጎንጨት ብሎ። እሷ የቀረበላትን ጠጅ አልነካችውም። “ይጠጡ እንጂ” እንዳይላት ድፍረት መሰለው።
“እኔ ለነገሩ ሰው ማለት ምን ማለት ነው ብየ የጠየቅሁት እንዳው
ያገራችን ነገር አሳስቦኝ ነው። ይረዳሉ ብለህ ያሰብኻቸው ሁሉ
አንተንም አገርንም ሲጎዱ ስታይ ይገርማል። ሰላም ጠፋ።”
“ርግጥ ነው ... ርግጥ ነው እቴጌ... ሁላችንን ሚያሳስበን ይኸው ነው” አለ፣ በሐሳብ ተውጦ ሳይመልስላት በመቅረቱ ደንገጥ ብሎ። “እቴጌ በእርስዎና በንጉሥ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ዘመን ደግ ግዝየ አለፈ።
እናንተ ደግ ጥሩ ነበራችሁና ግዝየውን ደግ... ጥሩ አረጋችሁ።
አዋቂው እንዳለው እኛ መልካም ስንሆን ግዝየውም መልካም ይሆናል። ከቶም ያገሩ ንጉሥ ወይም ገዥ ደግ ተኾነ ሕዝቡም ደግ ነው ሚኾን፤ገዥው ተከፋም ሕዝቡም አብሮ ይከፋል። “እስመ ከመ መኰንና ለአገር ከማሁ ይገብሩ እለ ውስቴታ ይላል፤ አገረ ገዥው የሚያደርገውን ነገር ሁሉ በአገሪቱ ያሉ ያደርጋሉ ሲል ነው። መቸም በሩቅም ቢሆን
ስለእርስዎ ደግነት ብዙ ሰምቻለሁ ሁሉ ያመሰግንዎታል። እርስዎ
ለምለም ልቡና ያለዎና ልበ ጽኑ በመሆንዎ አምላክ መንግሥትዎን
ሥሙር አርጎልዎ፣ አቅንቶልዎ ለዐርባ ዓመት ገደማ ሰላም የመላበት ዘመን ሰጡን። አጤ ኢያሱ ካደጉ በኋላ እርስዎም እሳቸውም ባሳያችሁት
ትጋት እፎይ ብለን ዐርፈን አለሥጋት ተማርን፤ ሠራን። አሁን ግን ይኸው ተኝተን ሳይሆን በቁማችን እንባንናለን።”
“የኛ ዘመን ... መቸም ዕድለኛ ሁነን...”
“ዕድለኛስ አይበሉ እቴጌ! ነገርዎን አቋረጥሁ እንጂ..”
“ኧረ ግዴለህም እህትህ ነኝ እንደ ሹመኛ አትሽቆጥቆጥብኝ
አለችው፣ በፈገግታና በሚያቀራርብ ቅላጼ።
“አይ ግዴለዎትም ቀስ እያልሁ እዘናለሁ፤ ክብረት ይስጥልኝ። ደሞስ መሽቆጥቆጥ ለካህናተ ደብተራ ወግ ማዶል” ብሎ ፈገግታውን እንደያዘ ነገሩን ቀጠለ። “ንጉሥ ኢያሱ ልዥ በነበሩ ግዝየ ያን ሁሉ ትጋትዎን አይተን... ሰምተን ማልነበር? እሳቸውም ካደጉ በኋላ ተባብራችሁ
አገራችንን ሰላም አረጋችሁ፤ ደከማችሁላት። የጥጋብ ዘመን ሰጣችሁን።ሰዉም ወደዳችሁ። የሰው መውደድ ብል አጤ በካፋስ እያሉ ቢሆን እርስዎ ተወዳጅ ነበሩ። ጠንካራም ይባሉ ነበር። ይኸ ዛዲያ እንደምን ስለ ዕድል ይቆጠራል? እኔማ ቢጠይቁኝ ዕድል ሚሄድበትን ያቃል እላለሁ። ያኔ በለጋነቴ እምብዛም አይገባኝም ነበር። አንዴ ዛዲያ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ሔኖክ ዕድል ከሰማይ አይወድቅም' ዕድል እንደ ሥዕል ነው። የሚገባውጋ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሆኖ
ማይጠብቀውጋ ኣይኸድም' ብለውኝ ያውቃሉ።”
“እኔም እሚታ ዮልያና ዕድል ኸሰማይ ይወድቃል?' ስትል
ሰምቻለሁ። አሳቡ አንድ ነው። እኔ ግን ዕድል ሚሰጠን እዝጊሃር ነው
እላለሁ።”
“ግና ማንችለውን አይሰጠንም። ማንችለውን ሰጥቶን ብንወድቅ...
ሳንችል ብንቀር ማን ሊጠየቅ ነው?”
“አየ ጥላዬ... ሰውን ትፈታተናለህ መሰል” አለችና ከት ብላ ሳቀች።
“እቴጌ... በመንበርዎ ትንሽ በቆዩ ኑሮ አሁን ኸመጣብን መቅሰፍት
እንድን ነበር” አለ፣ ጨዋታውን ለውጦ። “ድኻውም እኮ ቢሆን እርስዎን ተገን አርጎ ነበር የኖረ። ዛሬ ለሱ ሚያስብለት ማን አለው? ጉያዎ ደብቀው ያቆይዋትም አገር ይኸው አሁን መፈንጫ ሆነች። አሳቢ ጠፋ። አዋቂ ጠፋ። የዕውቀት ውጤቱ ሰላምና ቅንነት ነው፤ የዕውቀት ደግነቱ ማስተዋል ነው ብሎም ማልነበር ፈላስፋው? አሁን ሰላምም፣ ቅንነትም፣ ማስተዋልም የለ።”
ምንትዋብ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች። “አእምሮ ለነፍስ መዳኒቷ ነው፤ የልብ ሽልማት አእምሮ ነው' ይል የለ ፈላስፋው?”
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ለዓመታት በርካታ የመንፈስ ድል ስትቀዳጅ ቆይታ ልጇ ከሞተ በኋላ፣ ይኸው ድል ወደ ሽንፈት የተቀየረ በመሰላት ሰዐት እሱን በማግኘቷ ልቧ ተነሳስቶ ኸንግዲህ ሞት እንጂ ሌላ አይለየንም አለች።
አስተናጋጅ ወይን ጠጅ አምጥቶ ቀድቶላቸው ወጣ።
“ጠጣ እስቲ!” አለችው፣ ፈገግ ብላ።
የትካዜው ድባብ ተገፈፈ።
“ለመሆኑ ሥዕል እንዴት ዠመርህ?”
“ቋራ ሁኘ ነው የዠመርሁት” አለና ስለግድግዳው ታሪክ ነገራት።
ከት ብላ ሳቀች። “ሥዕል ትሥል እንደነበር ዛዲያ እንዴት
አላወቅሁም?”
“አባባ ለምሠራው ነገር ቁብ ሰጥተውት አያውቁም ነበር። ወዲያው ያጠፉት ነበረ። ቋራን ትቸ ጐንደር ዘልቄ እመኝ የነበረውን ሥዕል መማር ዠመርሁ። ኋላም ደብረ ወርቅ ማርያም ኸድሁ። መቸም በርስዎና በንጉሥ ኢያሱ ዘመን ሥዕል አደገ። ጐንደር ውስጥ የባሕር ማዶ ሰዎች ኸመጡ ወዲያ ሥዕል ለውጥ ኣምጥቶ ነበረ...” ብሎ ከጠጁ
ተጎነጨ።
“እንዴት?”
“የቀድሞዎቹን ሥዕሎች ያስተዋሉ እንደሆን መለኮታዊ ይዘት
ያላቸውና ታሪክ ተራኪ ነበሩ። ኋላ ግን መለኮታዊ ብቻ ሳይሆን ሥዕል ወደ ሰው ወረደ። ሥጋ ለባሾች... ነገሥታት ሚሣሉበት ዘመን ላይ መጣን። የቀለም አጠቃቀም ሁሉ ለውጥ አመጣ። መቸም የአጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመንም በትምርትም ሆነ በሥዕል ብዙ ለውጥ የመጣበት
ዘመን ነበር። ቁም ጸሐፊው፣ ደብተራው ቁጭ ማለት ያመጣበት ግዝየ ስለነበረ ቁጭ ሲባል ፉክክር፣ ክርክርና አሳብ ለአሳብ መለዋወጥ መጣ።እንዲያም ብሎ አንድምታ ትምርት ተዠመረ። ይኸ አሳብን መግለጽ ወደ ሥዕለም መጣ።”
“እንዴት ያለ ነገር ነገርኸኝ? ሁሉ ሚሆነው በግዝየው ነው መሰለኝ
ብላ ፈገግ አለች።
“አዎ ሁሉ ሚሆነው በግዝየና በቦታ ነው። አለግዝየውና አለቦታው ሚሆን ምን አለ?”
“ግዝየ ምንድነው?”
“ግዝየ እኛ ነን።”
“የግዝየ ነገር ይገርመኛል።”
“የሰው ነገር ይገርመኛል ማለትዎ ነው? ግዝየን ሆነ ቦታን ምንፈጥር
እኛ ሰዎች እኮ ነን። እዝጊሃር ምድርና ሰማይን ፈጠረ። እኛ ደሞ
ግዝየንና ቦታን ፈጠርን። ግዝየ ሆነ ቦታ አለኛ የሉም? ቦታም ግዝየም እኛ ነን። እኛ ጥሩ ስንሆን ግዝየም ጥሩ ይሆናል። እኛ ጥሩ ስንሆን የሰማዩም ደስ ይለዋል፣ ምድርም ለፍጥረታት ሁሉ ምቹ ቦታ
ትሆናለች።”
“አሳብህ ገባኝ። ግዝየ ሳይሆን እኛ ነን ምንገርመው ማለትህ ነው?
እንግዲያማ የሰው ነገር ይገርመኛል።”
“አየ እቴጌ ዝናዎን ሰምቻለሁ። ሊቃውንት ሆኑ ካህናት ያደንቅዎታል።እርስዎ የጠለቀ ዕውቀት... ትምርት ያለዎ... አንደበታምና ታሪክ
አስተካካይ... የሰው ባሕርይ ይግረምዎ?”
“አንተ የሥዕል ንጉሥ፣ የሰማዩንም የምድሩንም ብራና ላይ
ምታስቀምጥ እስቲ ንገረኝ። ሰው ማለት ምን ማለት ነው?”
“እቴጌ ሰው ማለት ምን ማለት እንደሆነ ኻወቅሁማ ፈጣሪን ሆንሁ።እኛ ሰዎች መሆን የነበረብን ሚዛኑ ከፍ አለና እኛ አነስን። መሆን ሚገባንን መሆን አልቻልንም። መቸም ጉድለት አለን ብንል ፈጣሪ ጉድለት ያለው ፈጠረ ማለት ይሆንብናል። ሙሉ ግን ማዶለን።”
“ዛዲያ የተሟላን መሆን ቢያቅተን፣ ኸሚዛኑ ብንጎድል፣ ለመሙላት
አንጥርምን?”
“ቢሆንልንማ እንዲያ ነበር።”
“እኔስ እንዲያው በተለየ አሁን ያለንበትን ሳስብ ክፋትና ደግነት
አብረውን የተወለዱ ናቸው ነው እምል።”
“ስለ ሰው ባሕርይ ተመራምረን ምንደርስበት አይመስለኝም::”
አለ ጥላዬ ከጠጁ አሁንም ጎንጨት ብሎ። እሷ የቀረበላትን ጠጅ አልነካችውም። “ይጠጡ እንጂ” እንዳይላት ድፍረት መሰለው።
“እኔ ለነገሩ ሰው ማለት ምን ማለት ነው ብየ የጠየቅሁት እንዳው
ያገራችን ነገር አሳስቦኝ ነው። ይረዳሉ ብለህ ያሰብኻቸው ሁሉ
አንተንም አገርንም ሲጎዱ ስታይ ይገርማል። ሰላም ጠፋ።”
“ርግጥ ነው ... ርግጥ ነው እቴጌ... ሁላችንን ሚያሳስበን ይኸው ነው” አለ፣ በሐሳብ ተውጦ ሳይመልስላት በመቅረቱ ደንገጥ ብሎ። “እቴጌ በእርስዎና በንጉሥ ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ዘመን ደግ ግዝየ አለፈ።
እናንተ ደግ ጥሩ ነበራችሁና ግዝየውን ደግ... ጥሩ አረጋችሁ።
አዋቂው እንዳለው እኛ መልካም ስንሆን ግዝየውም መልካም ይሆናል። ከቶም ያገሩ ንጉሥ ወይም ገዥ ደግ ተኾነ ሕዝቡም ደግ ነው ሚኾን፤ገዥው ተከፋም ሕዝቡም አብሮ ይከፋል። “እስመ ከመ መኰንና ለአገር ከማሁ ይገብሩ እለ ውስቴታ ይላል፤ አገረ ገዥው የሚያደርገውን ነገር ሁሉ በአገሪቱ ያሉ ያደርጋሉ ሲል ነው። መቸም በሩቅም ቢሆን
ስለእርስዎ ደግነት ብዙ ሰምቻለሁ ሁሉ ያመሰግንዎታል። እርስዎ
ለምለም ልቡና ያለዎና ልበ ጽኑ በመሆንዎ አምላክ መንግሥትዎን
ሥሙር አርጎልዎ፣ አቅንቶልዎ ለዐርባ ዓመት ገደማ ሰላም የመላበት ዘመን ሰጡን። አጤ ኢያሱ ካደጉ በኋላ እርስዎም እሳቸውም ባሳያችሁት
ትጋት እፎይ ብለን ዐርፈን አለሥጋት ተማርን፤ ሠራን። አሁን ግን ይኸው ተኝተን ሳይሆን በቁማችን እንባንናለን።”
“የኛ ዘመን ... መቸም ዕድለኛ ሁነን...”
“ዕድለኛስ አይበሉ እቴጌ! ነገርዎን አቋረጥሁ እንጂ..”
“ኧረ ግዴለህም እህትህ ነኝ እንደ ሹመኛ አትሽቆጥቆጥብኝ
አለችው፣ በፈገግታና በሚያቀራርብ ቅላጼ።
“አይ ግዴለዎትም ቀስ እያልሁ እዘናለሁ፤ ክብረት ይስጥልኝ። ደሞስ መሽቆጥቆጥ ለካህናተ ደብተራ ወግ ማዶል” ብሎ ፈገግታውን እንደያዘ ነገሩን ቀጠለ። “ንጉሥ ኢያሱ ልዥ በነበሩ ግዝየ ያን ሁሉ ትጋትዎን አይተን... ሰምተን ማልነበር? እሳቸውም ካደጉ በኋላ ተባብራችሁ
አገራችንን ሰላም አረጋችሁ፤ ደከማችሁላት። የጥጋብ ዘመን ሰጣችሁን።ሰዉም ወደዳችሁ። የሰው መውደድ ብል አጤ በካፋስ እያሉ ቢሆን እርስዎ ተወዳጅ ነበሩ። ጠንካራም ይባሉ ነበር። ይኸ ዛዲያ እንደምን ስለ ዕድል ይቆጠራል? እኔማ ቢጠይቁኝ ዕድል ሚሄድበትን ያቃል እላለሁ። ያኔ በለጋነቴ እምብዛም አይገባኝም ነበር። አንዴ ዛዲያ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ሔኖክ ዕድል ከሰማይ አይወድቅም' ዕድል እንደ ሥዕል ነው። የሚገባውጋ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሆኖ
ማይጠብቀውጋ ኣይኸድም' ብለውኝ ያውቃሉ።”
“እኔም እሚታ ዮልያና ዕድል ኸሰማይ ይወድቃል?' ስትል
ሰምቻለሁ። አሳቡ አንድ ነው። እኔ ግን ዕድል ሚሰጠን እዝጊሃር ነው
እላለሁ።”
“ግና ማንችለውን አይሰጠንም። ማንችለውን ሰጥቶን ብንወድቅ...
ሳንችል ብንቀር ማን ሊጠየቅ ነው?”
“አየ ጥላዬ... ሰውን ትፈታተናለህ መሰል” አለችና ከት ብላ ሳቀች።
“እቴጌ... በመንበርዎ ትንሽ በቆዩ ኑሮ አሁን ኸመጣብን መቅሰፍት
እንድን ነበር” አለ፣ ጨዋታውን ለውጦ። “ድኻውም እኮ ቢሆን እርስዎን ተገን አርጎ ነበር የኖረ። ዛሬ ለሱ ሚያስብለት ማን አለው? ጉያዎ ደብቀው ያቆይዋትም አገር ይኸው አሁን መፈንጫ ሆነች። አሳቢ ጠፋ። አዋቂ ጠፋ። የዕውቀት ውጤቱ ሰላምና ቅንነት ነው፤ የዕውቀት ደግነቱ ማስተዋል ነው ብሎም ማልነበር ፈላስፋው? አሁን ሰላምም፣ ቅንነትም፣ ማስተዋልም የለ።”
ምንትዋብ በመስማማት ራሷን ነቀነቀች። “አእምሮ ለነፍስ መዳኒቷ ነው፤ የልብ ሽልማት አእምሮ ነው' ይል የለ ፈላስፋው?”
👍14