#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ብጠጣለት የሚጎዳኝ ይመስልሃል?"
ወራጅ ውሃ እኮ ነው። እፅዋት በልምላሜ ፈክተው ጎንበስ ቀና እያሉ የሚወዛወዙበት አራዊት እየፈነደቁ የሚፈነጥዙበት
ዋኔ ዳክዬዎች ብቅ ጥልቅ እያሉ ተጎንጭተው የሚንሳፈፉበት ወደ
ሰማዬ ሰማያት ጉነው የሚበሩበት... ውሃ የሚጎዳሽ አይመስለኝም፡፡
ስለዚህ ይህን ከብክለት ነፃ የሆነ ውሃ በእጆችሽ መዳፍ እያፈሰሽ ተጎጭው ማሬ አላት፡፡
ኮንችት እድሜዋ ባጠረ ግርምታ ተመሰከተችውና፡-
“ይገባኛል ገና አልተበከለም ገና አልቆሸሽም… ስልጣኔ
ኩሉን አልጣላበትም ቅርሻቱን አልደፋበትም… በእርግጥ ሳልፈራ መጠጣት ነበረብኝ ብላ በርከክ ብላ ሁለት እጆችዋን እንደ አካፋ አሹላ በእፍኝዋ የቀዳችውን ውሃ እንደ ወፎቹ አንጋጣ ወደ ጉሮሮዋ
አንቀረቆረችው፡ ጎርፍ መሳዩ ንፁህ ውሃ ጉሮሮዋን እያቀዘቀዛት ቁልቁል ወረደ ደስ አላት ጣማት፡፡ ስለዚህ እየደጋገመች ተጎነጨችው፡፡
ቀና ብላ አየች ሰማያዊው ሰማይ ተውቧል ! ወደ ዳርና
ዳር እፅዋትን ተመለከተች የቆላ ዋንዛ፡ ጥቁር እንጨት እንኮይ ጠዪ. ቃጫ. . . በአረንጓዴ ልምላሜ ተሞልተው ምድሯን
አስውበዋታል፡ ጉጉት ድርጭት ጂግራ ቆቅ… ወፎች ይዘምራሉ ይጯሀሉ ይስቃሉ… አቦ ሽማኔ አንበሳው ቆርኪው ዝንጀሮው ጦጣና ጉሬዛው. በእዕዋት ስር ሲርመሰመሱ፡ በእዕዋት ቅርንጫፎች
ላይ እየተንጨዋለሉ ሲወናጨፉ ይታያሉ፡፡
እባቡ እንሽላሊቱ… በዕፅዋት ግንድ
ይልወሰወሳሉ፡፡ ኦሞ ወንዝ ላይ አዞው ራሱን አውጥቶ ይንሳፈፋል፧አሶች ብቅ እያሉ ጥቡሉቅ ይላሉ….
ተፈጥሮ እንደ ሙሽራ ደምቃለች አምራለች ፈክታለች...እንደ ማራኪው የአዳም ዘመን ገነት ኑሮ! ኮንችት ያን ድንቅ ውበት
በአይኗ በጆሮዋ ባጠቃላይ በስሜት ሕዋሶችዋ እየኮረሻሽመች በላችው እንዳያንቃት ከወንዙ ውሃ ተጎነጨለት….
“…ገና ካሁኑ አያቴ ያጣውን ተረዳሁለት" አለች ወደ ሶራ
ዙራ፡
“ድንግል ውበትን ነፃነትን እርጋታን… ነበር አያቴ ያጣው'' እንባዋ በአይኖችዋ ሞላ፡፡ “ሁካታ የሌለበት ዓለም አንዱ ሌላውን
የማይጎዳበት ተፈጥሮ ቅኝቱ የተዋሃደ ቅላፄ ነበር አያቴ ያጣው ለካ" እየሳቀች አለቀሰች፡፡ እንባዋ እየፈሰሰ ጥርሶችዋ ግን ተገለጡ
ሰዎች እውነተኛ ስሜት ሲሰማቸው ስሜታቸው ይደበላለቃል" ይህች
ፕላኔት የሚለቀስባት ካልያም የሚሳቅባት ብቻ አይደለችም፤ ደስታና
ሐዘን ሣቀና ልቅሶ እንደ ሳንቲም ገፅታ አብረው የሚኖሩባት ናት፤እና እውነተኛው የተፈጥሮ ስሜት ኮንችት ላይም ደረሰ
እንደ አያቷ ትናንትን ዛሬ ላይ ቁማ አለመችው፧ እንደ
ልጆችዋ ዛሬ ላይ ቆማ ነገን አሰበችው ተፈጥሮ እንደ ሰው አታረጅ ይሆናል እሚያቆሽሻት ሰው እስካለ ግን እንደ ትናንቱ ዛሬ
አታምርም፡ እንደ ዛሬው የውበት ፀዳሏ ለነገ አይደርስም፡፡ እና
ኮንችት ከመሃል ሆነች ከኢትዮጵያዊው አያቷና ካልወለደችው ልጅዋ መካከል!
ኮንችት የእፎይታ ትንፋሽዋን አንቦለቦለችና ሃዘንና ደስታዋን ሙሉ በሙሉ የተካ ፈገግታ ለውቡ ተፈጥሮ አበርክታ ሶራን ተመለከተችው፡፡
ኮንችት እንደ ከብቶች፥ እንደ አዕዋፍ እንደ እፅዋት ራቁቷን ብትሆን ትመረጣለች በተለይ በእንዲህ ዓይነቱ ተፈጥሮአዊ ተፈጥሮ… መመሳሰል ያረካታል።
ፓንትና ጡት ማሲያዣ ሲቀር
ሁሉንም ልብሷን አወለቀችው ልብስ ገመናን ሃፍረተ ሥጋን መሸፈኛ ነው።
እውነተኛው ተፈጥሮ ግን ገመና ሃፍረተ ስጋ የለም፡፡ ተፈጥሮ ገነት ናት አዳምና ሄዋን ዕፀ በላሷን ከመብላታቸው በፊት
እንደነበሩት።
ቤጫ መስመር በጎንና ጎኗ የተጋደመባት ሰማያዊ ቀለም ያላት የፕላስቲክ ጀልባ እየተጀነነ በኩራት ቁልቁል ይሁን ሽቅብ
መፍስሱ ግራ በሚያጋባው የኦሞ ወንዝ ላይ እንደ ቄብ ዶሮ ቂብ ብላ በአፍንጫዋ ውሃውን ግራና ቀኝ እየከፈለች ትንሳፈፋለች፡
ኮንችት አጠር ያለውንና ቢጫውን መቅዘፊያ ካስቀመጠችበት
አንስታ ከሶራ ጎን ካለው ቦታ ቁጭ ብላ በግራ እጅዋ የመቅዘፊያውን እጀታ ጨብጣ ውሃውን ሶስቴ
ገፋችና ወደ ሶራ ዞራ ፈገግ አለች፡፡ ሶራም በመቅዘፊያው ውሃውን
ወደ ኋላ እየገፋ ፈገግ አለላት፡፡
ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመችና ወደ ወንዙ ዘለለች ወደ ኦሞ ቁልቁል ሰጠመች፤ እግርና እጅዋ በስልት እየተንቀሳቀ
እንደ አሶች ውስጥ ለውስጥ ዋኘች፡፡
ሶራ መቅዘፉን አቁሞ ኮንችት ካለ ህይወት አድን ጃኬት ባዶዋን ወንዝ ውስጥ በመግባቷ ደነገጠ፡፡ ልብሱን ከመቅጽበት አውልቆ አያት ገና ብቅ አላለችም፡፡ ዘሎ ውሃው ውስጥ ገባና
በውሃው ውስጥ ለውስጥ ፈለጋት፡፡ ስማያዊዋ ጀልባ ግራ ቀኝ ተወዛወዘ ቀስ በቀስ ተረጋግታ ተንሳፈፈች፡፡ ሶራ የሆነ ድምፅ ሰማና
ሽቀብ ወደላይ ቀዘፈ:
እህ! እህ. በድካም እያቃሰተች ኮንችት ትስቃለች፡፡እሱም አብሯት ሳቀ፡ ውሃው ውስጥ ተጠጋጉ፡ ሳቀ ሳቀች ፍርስ
እያሉ ተሳሳቁ ውሃ ተራጩ የአፍሪካ ንሥር አየሩ ላይ
ይንሳፈፋል፡፡ ከዳር በኩል ውሃ ሲጠጡ የነበሩት ዝሆኖች በአድናቆት
ተመለከቷቸው
“ዝሆን የአፍሪካ ዝሆን ጆሮ ሰፊው የዝሆን ጉዞ' በሚል
በልዕልት ሚድታውን ታናል' ስርከስ ላይ ከቀረቡት ዝሆኖች ሁሉ እጅግ የገዘፈ' ብላ ኮንችት ዝሆኖችን በአድናቆት ተመሰከተቻቸው፡፡
ሶራና ኮንችት ጀልባዋ ላይ ወጡ፡፡ ሰውነታቸው በውሃ
ነጠብጣብ ተሞልቷል፡ ዝሆኖች ለምለም ጨሌ ሣር ከሚታይበት ሜዳ ወጣ አሉና አንድ ኮርማ ዝሆንና አንዲት ሴት ዝሆን መዳራት
ጀመሩ፡፡ ከጥቂት ማሽኮርመም በኋላ ወንዱ ዝሆን ያን ግዙፍ ሰውነቱን ወደ ላይ አንስቶ በኋላ እግሩ ቆመና የፊት እግሮቹን ሴቷ
ዝሆን ላይ ጭኖ የእንግሊዘኛውን ኤስ' ፊደል ቅርፅ ያለውን ብልቱን
እንደምንም ብሎ ሴቷ ብልት አስገባና ሰረራት፡፡
ኮንችትና ሶራ ያን ተፈጥሮአዊ ትርኢት አፋቸውን ከፍተው
ሲያዩ ላያቸው ላይ የነበረው የውሃ ነጠብጣብ ደረቀላቸው፡፡ የጫካው
የተፈጥሮ ድሪያ ሳባቸው፡፡ ተፈጥሮ ውስጥ የተፈጥሮ ድሪያ ያስጎመዣል ...
ኮንችት ለስላሳና ቀጥ ያሉ ጭኖችዋን አጥፋ የመቅዘፊያውን እጀታ አንስታ ለመቅዘፍ ጠምዘዝ ስትል ሰፋ ያለው ዳሌዋ ሰርጓዳው ወገቧ ጠባቡ ትከሻዋ ሰውነቷ ላይ የተለጠፈው ዞማ ፀጉሯን…
አየው! ተስገበገበ… ኮንችት እንዲህ የውበቷን ሰዲቃ ሲቋደስ ዞር ብላ ፈገግታዋን አከለችለት፡
ከወንዙ ውሃ ግራና ቀኝ ካሉት የውበት ፀዳሎች ጋር
የተጣጣመው ውበቷ እንደ ፍላፃ ሕሊናውን ወጋው፡፡ ዞር አለች እንደገና፤ ሶራ ከንፈሮቹን በቀስታ ግራና ቀኝ እንደ ላስቲክ እየለጠጠ
ዘርዘር ያሉ ጥርሶቹን አሳያት እሷም ፈገግ አለች ፈገግታዋ በመቀጣጠል ላይ ያለውን ስሜቱን ቤንዚን እንደጨመሩበት እሳት
ባንዴ ቦግ አደረገው፡፡ ሰደዱ እሷ ህሊናም በቅጽበት ደርሶ እሷንም ለበለባት…ሳይታወቃቸው እሳታቸውን ለማብረድ ሁለቱም
ከንፈሮቻቸውን በምላሳቸው አረጠቡ የአይናቸው ቆብ ቁልቁል እየወረደ ተከደነ… ዝሆኑ ሽቅብ ተነሳ. ሴቷ ተጠጋችው፡
የሚመነጭቀው እንዳለ ሁሉ ጥብቅ አድርጎ አቀፋት… ዝሆኑ!
አእዋፍ ያፏጫሉ ጀልባዋ
ትንሳፈፋለች እንቁራሪቶች
ያንቆርራሉ ኮንችት የሶራን
የእጅ ጡንቻዎች ሳም ሳም ስታደርግለት እሱ አካሏን እየላሰ ሎሚውን በእጁ ጣቶች እያሻሽ ከንፈሩና ከንፈሯ ተገናኘ ኮንችት ይበልጥ እየሰረሰረች ተጠጋችው !
ያኔ! ጎርበጥ ያለው ነገር ቆረቆራት የቆረቆራትን የቀኝ እጅዋን ሰዳ ከተደበቀበት ስታወጣው እንደ ህፃን ልጅ ፈነደቀ…
ኦሞ ወንዝ በኵራት ይፈሳል እፅዋት በንፋስ ይወዛወዛሉ
+ፈጥሮ አራዊትና አዕዋፍ ይዳራሉ:: ብርጉዱ እጣኍ ጠጅ ሳሩ ጤናዳሙ ጽጌረዳው የበረሃ እጣነ አካባቢውን አልባብ አልባብ
እሸተ† ድንቅ የተፈጥሮ ህይወት ታምር ይታያል!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ብጠጣለት የሚጎዳኝ ይመስልሃል?"
ወራጅ ውሃ እኮ ነው። እፅዋት በልምላሜ ፈክተው ጎንበስ ቀና እያሉ የሚወዛወዙበት አራዊት እየፈነደቁ የሚፈነጥዙበት
ዋኔ ዳክዬዎች ብቅ ጥልቅ እያሉ ተጎንጭተው የሚንሳፈፉበት ወደ
ሰማዬ ሰማያት ጉነው የሚበሩበት... ውሃ የሚጎዳሽ አይመስለኝም፡፡
ስለዚህ ይህን ከብክለት ነፃ የሆነ ውሃ በእጆችሽ መዳፍ እያፈሰሽ ተጎጭው ማሬ አላት፡፡
ኮንችት እድሜዋ ባጠረ ግርምታ ተመሰከተችውና፡-
“ይገባኛል ገና አልተበከለም ገና አልቆሸሽም… ስልጣኔ
ኩሉን አልጣላበትም ቅርሻቱን አልደፋበትም… በእርግጥ ሳልፈራ መጠጣት ነበረብኝ ብላ በርከክ ብላ ሁለት እጆችዋን እንደ አካፋ አሹላ በእፍኝዋ የቀዳችውን ውሃ እንደ ወፎቹ አንጋጣ ወደ ጉሮሮዋ
አንቀረቆረችው፡ ጎርፍ መሳዩ ንፁህ ውሃ ጉሮሮዋን እያቀዘቀዛት ቁልቁል ወረደ ደስ አላት ጣማት፡፡ ስለዚህ እየደጋገመች ተጎነጨችው፡፡
ቀና ብላ አየች ሰማያዊው ሰማይ ተውቧል ! ወደ ዳርና
ዳር እፅዋትን ተመለከተች የቆላ ዋንዛ፡ ጥቁር እንጨት እንኮይ ጠዪ. ቃጫ. . . በአረንጓዴ ልምላሜ ተሞልተው ምድሯን
አስውበዋታል፡ ጉጉት ድርጭት ጂግራ ቆቅ… ወፎች ይዘምራሉ ይጯሀሉ ይስቃሉ… አቦ ሽማኔ አንበሳው ቆርኪው ዝንጀሮው ጦጣና ጉሬዛው. በእዕዋት ስር ሲርመሰመሱ፡ በእዕዋት ቅርንጫፎች
ላይ እየተንጨዋለሉ ሲወናጨፉ ይታያሉ፡፡
እባቡ እንሽላሊቱ… በዕፅዋት ግንድ
ይልወሰወሳሉ፡፡ ኦሞ ወንዝ ላይ አዞው ራሱን አውጥቶ ይንሳፈፋል፧አሶች ብቅ እያሉ ጥቡሉቅ ይላሉ….
ተፈጥሮ እንደ ሙሽራ ደምቃለች አምራለች ፈክታለች...እንደ ማራኪው የአዳም ዘመን ገነት ኑሮ! ኮንችት ያን ድንቅ ውበት
በአይኗ በጆሮዋ ባጠቃላይ በስሜት ሕዋሶችዋ እየኮረሻሽመች በላችው እንዳያንቃት ከወንዙ ውሃ ተጎነጨለት….
“…ገና ካሁኑ አያቴ ያጣውን ተረዳሁለት" አለች ወደ ሶራ
ዙራ፡
“ድንግል ውበትን ነፃነትን እርጋታን… ነበር አያቴ ያጣው'' እንባዋ በአይኖችዋ ሞላ፡፡ “ሁካታ የሌለበት ዓለም አንዱ ሌላውን
የማይጎዳበት ተፈጥሮ ቅኝቱ የተዋሃደ ቅላፄ ነበር አያቴ ያጣው ለካ" እየሳቀች አለቀሰች፡፡ እንባዋ እየፈሰሰ ጥርሶችዋ ግን ተገለጡ
ሰዎች እውነተኛ ስሜት ሲሰማቸው ስሜታቸው ይደበላለቃል" ይህች
ፕላኔት የሚለቀስባት ካልያም የሚሳቅባት ብቻ አይደለችም፤ ደስታና
ሐዘን ሣቀና ልቅሶ እንደ ሳንቲም ገፅታ አብረው የሚኖሩባት ናት፤እና እውነተኛው የተፈጥሮ ስሜት ኮንችት ላይም ደረሰ
እንደ አያቷ ትናንትን ዛሬ ላይ ቁማ አለመችው፧ እንደ
ልጆችዋ ዛሬ ላይ ቆማ ነገን አሰበችው ተፈጥሮ እንደ ሰው አታረጅ ይሆናል እሚያቆሽሻት ሰው እስካለ ግን እንደ ትናንቱ ዛሬ
አታምርም፡ እንደ ዛሬው የውበት ፀዳሏ ለነገ አይደርስም፡፡ እና
ኮንችት ከመሃል ሆነች ከኢትዮጵያዊው አያቷና ካልወለደችው ልጅዋ መካከል!
ኮንችት የእፎይታ ትንፋሽዋን አንቦለቦለችና ሃዘንና ደስታዋን ሙሉ በሙሉ የተካ ፈገግታ ለውቡ ተፈጥሮ አበርክታ ሶራን ተመለከተችው፡፡
ኮንችት እንደ ከብቶች፥ እንደ አዕዋፍ እንደ እፅዋት ራቁቷን ብትሆን ትመረጣለች በተለይ በእንዲህ ዓይነቱ ተፈጥሮአዊ ተፈጥሮ… መመሳሰል ያረካታል።
ፓንትና ጡት ማሲያዣ ሲቀር
ሁሉንም ልብሷን አወለቀችው ልብስ ገመናን ሃፍረተ ሥጋን መሸፈኛ ነው።
እውነተኛው ተፈጥሮ ግን ገመና ሃፍረተ ስጋ የለም፡፡ ተፈጥሮ ገነት ናት አዳምና ሄዋን ዕፀ በላሷን ከመብላታቸው በፊት
እንደነበሩት።
ቤጫ መስመር በጎንና ጎኗ የተጋደመባት ሰማያዊ ቀለም ያላት የፕላስቲክ ጀልባ እየተጀነነ በኩራት ቁልቁል ይሁን ሽቅብ
መፍስሱ ግራ በሚያጋባው የኦሞ ወንዝ ላይ እንደ ቄብ ዶሮ ቂብ ብላ በአፍንጫዋ ውሃውን ግራና ቀኝ እየከፈለች ትንሳፈፋለች፡
ኮንችት አጠር ያለውንና ቢጫውን መቅዘፊያ ካስቀመጠችበት
አንስታ ከሶራ ጎን ካለው ቦታ ቁጭ ብላ በግራ እጅዋ የመቅዘፊያውን እጀታ ጨብጣ ውሃውን ሶስቴ
ገፋችና ወደ ሶራ ዞራ ፈገግ አለች፡፡ ሶራም በመቅዘፊያው ውሃውን
ወደ ኋላ እየገፋ ፈገግ አለላት፡፡
ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመችና ወደ ወንዙ ዘለለች ወደ ኦሞ ቁልቁል ሰጠመች፤ እግርና እጅዋ በስልት እየተንቀሳቀ
እንደ አሶች ውስጥ ለውስጥ ዋኘች፡፡
ሶራ መቅዘፉን አቁሞ ኮንችት ካለ ህይወት አድን ጃኬት ባዶዋን ወንዝ ውስጥ በመግባቷ ደነገጠ፡፡ ልብሱን ከመቅጽበት አውልቆ አያት ገና ብቅ አላለችም፡፡ ዘሎ ውሃው ውስጥ ገባና
በውሃው ውስጥ ለውስጥ ፈለጋት፡፡ ስማያዊዋ ጀልባ ግራ ቀኝ ተወዛወዘ ቀስ በቀስ ተረጋግታ ተንሳፈፈች፡፡ ሶራ የሆነ ድምፅ ሰማና
ሽቀብ ወደላይ ቀዘፈ:
እህ! እህ. በድካም እያቃሰተች ኮንችት ትስቃለች፡፡እሱም አብሯት ሳቀ፡ ውሃው ውስጥ ተጠጋጉ፡ ሳቀ ሳቀች ፍርስ
እያሉ ተሳሳቁ ውሃ ተራጩ የአፍሪካ ንሥር አየሩ ላይ
ይንሳፈፋል፡፡ ከዳር በኩል ውሃ ሲጠጡ የነበሩት ዝሆኖች በአድናቆት
ተመለከቷቸው
“ዝሆን የአፍሪካ ዝሆን ጆሮ ሰፊው የዝሆን ጉዞ' በሚል
በልዕልት ሚድታውን ታናል' ስርከስ ላይ ከቀረቡት ዝሆኖች ሁሉ እጅግ የገዘፈ' ብላ ኮንችት ዝሆኖችን በአድናቆት ተመሰከተቻቸው፡፡
ሶራና ኮንችት ጀልባዋ ላይ ወጡ፡፡ ሰውነታቸው በውሃ
ነጠብጣብ ተሞልቷል፡ ዝሆኖች ለምለም ጨሌ ሣር ከሚታይበት ሜዳ ወጣ አሉና አንድ ኮርማ ዝሆንና አንዲት ሴት ዝሆን መዳራት
ጀመሩ፡፡ ከጥቂት ማሽኮርመም በኋላ ወንዱ ዝሆን ያን ግዙፍ ሰውነቱን ወደ ላይ አንስቶ በኋላ እግሩ ቆመና የፊት እግሮቹን ሴቷ
ዝሆን ላይ ጭኖ የእንግሊዘኛውን ኤስ' ፊደል ቅርፅ ያለውን ብልቱን
እንደምንም ብሎ ሴቷ ብልት አስገባና ሰረራት፡፡
ኮንችትና ሶራ ያን ተፈጥሮአዊ ትርኢት አፋቸውን ከፍተው
ሲያዩ ላያቸው ላይ የነበረው የውሃ ነጠብጣብ ደረቀላቸው፡፡ የጫካው
የተፈጥሮ ድሪያ ሳባቸው፡፡ ተፈጥሮ ውስጥ የተፈጥሮ ድሪያ ያስጎመዣል ...
ኮንችት ለስላሳና ቀጥ ያሉ ጭኖችዋን አጥፋ የመቅዘፊያውን እጀታ አንስታ ለመቅዘፍ ጠምዘዝ ስትል ሰፋ ያለው ዳሌዋ ሰርጓዳው ወገቧ ጠባቡ ትከሻዋ ሰውነቷ ላይ የተለጠፈው ዞማ ፀጉሯን…
አየው! ተስገበገበ… ኮንችት እንዲህ የውበቷን ሰዲቃ ሲቋደስ ዞር ብላ ፈገግታዋን አከለችለት፡
ከወንዙ ውሃ ግራና ቀኝ ካሉት የውበት ፀዳሎች ጋር
የተጣጣመው ውበቷ እንደ ፍላፃ ሕሊናውን ወጋው፡፡ ዞር አለች እንደገና፤ ሶራ ከንፈሮቹን በቀስታ ግራና ቀኝ እንደ ላስቲክ እየለጠጠ
ዘርዘር ያሉ ጥርሶቹን አሳያት እሷም ፈገግ አለች ፈገግታዋ በመቀጣጠል ላይ ያለውን ስሜቱን ቤንዚን እንደጨመሩበት እሳት
ባንዴ ቦግ አደረገው፡፡ ሰደዱ እሷ ህሊናም በቅጽበት ደርሶ እሷንም ለበለባት…ሳይታወቃቸው እሳታቸውን ለማብረድ ሁለቱም
ከንፈሮቻቸውን በምላሳቸው አረጠቡ የአይናቸው ቆብ ቁልቁል እየወረደ ተከደነ… ዝሆኑ ሽቅብ ተነሳ. ሴቷ ተጠጋችው፡
የሚመነጭቀው እንዳለ ሁሉ ጥብቅ አድርጎ አቀፋት… ዝሆኑ!
አእዋፍ ያፏጫሉ ጀልባዋ
ትንሳፈፋለች እንቁራሪቶች
ያንቆርራሉ ኮንችት የሶራን
የእጅ ጡንቻዎች ሳም ሳም ስታደርግለት እሱ አካሏን እየላሰ ሎሚውን በእጁ ጣቶች እያሻሽ ከንፈሩና ከንፈሯ ተገናኘ ኮንችት ይበልጥ እየሰረሰረች ተጠጋችው !
ያኔ! ጎርበጥ ያለው ነገር ቆረቆራት የቆረቆራትን የቀኝ እጅዋን ሰዳ ከተደበቀበት ስታወጣው እንደ ህፃን ልጅ ፈነደቀ…
ኦሞ ወንዝ በኵራት ይፈሳል እፅዋት በንፋስ ይወዛወዛሉ
+ፈጥሮ አራዊትና አዕዋፍ ይዳራሉ:: ብርጉዱ እጣኍ ጠጅ ሳሩ ጤናዳሙ ጽጌረዳው የበረሃ እጣነ አካባቢውን አልባብ አልባብ
እሸተ† ድንቅ የተፈጥሮ ህይወት ታምር ይታያል!
👍19
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ የሶስተኛ ቀን የኦሞ ወንዝ ላይ ጉዟቸውን
ሲጀምሩ አየሩ ጨፍገግ ያለና ሰማዩ በጥቁር ዳመናዎች የተሸፈነ
ነበር፡፡
“ብንቆይ አይሻልም ኮንችት"
“አይ! አስቸጋሪውን ጉዞ ብንጋፈጠው ይሻላል፡፡ ምናልባት እየተጓዝን ዝናቡን ልናመልጠው እንችል ይሆናል፡፡ስለዚህ ቶሉ
መንቀሳቀሳችን ይሻላል፡"
“ወንዙ ላይ ዝናቡ ከያዘንስ?''
“ያኔ ከወንዙ ወጥተን ድንኳን ወጥረን እንጠለላለን፤ እዚህ
ሆኖ ሳይሞክሩ ተሸናፊ መሆን ግን አልፈልግም" አለችው፡
“እሽ በኔ በኩል ለጉዞ ዝግጁ ነኝ፡፡"
“ቆየኝ አንዴ” ብላው ለመፀዳዳት ወደ ጫካው ገባች፡፡ ሶራ የወንዝ ላይ ጉዞ አስደሳችም አስፈሪም እንደሆነ እየተረዳ መጥቷል፡፡
በተለይ ከመጀመሪው ቀን ቀጥሎ በነበረው ውድቅት ሌሊት አንበሶች የድሪያ ወቅታቸ በመሆኑ ከድንኳናቸው ብዙም ሳይርቅ እያገሱ ሲታገሉ
ኮንችትና ሶራ ከአሁ አሁን ላያችን ላይ ወጡ ገነጣጥለው ሊቀራመቱን ነው ሲሉ እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነው ያደሩት።
በሁሉተኛው ቀን ደግሞ ድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ ድንኳናቸውን በጎርፍ ውጦ ልብሳቸው በሙሉ ረጥቦ በዚያ ጥርስ
በሚፋጨው ብርድ እንደከበት ዛፍ ስር ጎን ለጎን ኵርም† ብለው
አንዱ በሌላው ትንፋሽ ሙቀት እየተጋሩ ነበር የመከራ ሌሊቱን ያሳለፉት።
ስለዚህ በነጋታው እስከ አጥንታችው ድረስ ዘልቆ የገባው ቆፈን እስኪወጣላቸው ፀይይ ላይ ተሰጥተው አረፈዱ ሰውነታቸውን ማዘዝና ማንቀሳቀስ ሲችሉ በጎርፍ የተዋጠውን ድንኳን ነቅለው
እቃውን አውጥተው… ፀሐይ ላይ አሰጡት ከዚያ ረጅም ሰዓት ቆይተው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ተነስተው ሰላሳ ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንቅልፍና ድካም ተጫጭኖአችው ስለነበር ደረቅ ዳቦና ብስኩት ብቻ ተመግበው ተኙ ልክ እንደሞተ ሰው ተኝተው
አድረው ሲነቁ ስማዩ የታቀፈውን ጥላሽት የመሰለ ዳመና እላያችው
ላይ ሊዘረግፈው ተዘጋጅቷል።
የሶራ ምርጫ ዝናቡን ማሳለፍ ይሻላል ነበር ኮንችት ግን ሃሳቡን ልተቀበለችውም።
አሁን መሄድ እንችላለን የህይወት ማዳኛ ጃኬቱን ልበስ ሱሪውን አውልቀውና የዋና ፓንትህን ታጠቅ አለችው ሶራ የተባለውን እየፈፀመ አያት የለበሰችው የዋና ፓንቷን ነው
ጭኖችዋ ከምን ጊዜውም በላይ አምረዋል: ከላይ ቀይ የህይወት ማዳኛ ጃኬቷን ቀይ ሄልሜቷን ደፍታ ዮጉዞ ቦርሳን ከጀርባሞ አዝላለች ሶራም እንደ እሷ ትጥቁን እያስመረ ስማዩን ቀና ብሎ
አየው ጠቁሯል
ጀልባዋን ውሃው ላይ ካሳረፉ በኋላ ድንኳናቸው
ምግባቸውን የማብሰያ እቃቸውን… ከጀልባው መሀል አስቀምጠው
በጣም አስፈላጊ የሆነውን ቁሳቁስ በጀርባ ቦርሳቸው አዘሉት፡፡ ከዚያ “አድሪፍት" የምትለው ጀልባ ላይ ያለውን ረጅም ገመድ ወገባቸው ላይ ካለው ሰፊ ቀበቶ ጋር አያያዙት፡፡
ጀልባዋ ላይ ወጥተው ሚዛናቸውን ለመጠበቅ ከኋላ በኩል ግራና ቀኙ ተቀመጡና መቅዘፊያቸውን አንስተው አውራ ጣታቸውን
በማንሳት ዝግጁ ተባባሉና ወደ ኦሞ ወንዝ መሃል ሄደው ቁልቁል ቀዘፉ
ሰማዩ እንደ ተቆጣ ነብር ማጉረምረም ጀመረ። ድንገት ሰማዩ በቀጫጭን የብርሃን ዝግዛግ እየተሰነጣጠቀ ብልጭታው
ይታይና ብራቁ ድብልቅልቅ ብሎ መጮሁ እየጨመረ ሄደ፡፡
“ኮንችት!” ብሎ ጠርቶ አያት፡፡ ቶሎ ቶሎ ትቀዝፋለች ለማምለጥ፡፡ ድክም ያላት መሆኑ በዚያ ቆፈን የሚወርደው ላቧ ያስታውቃል፡፡ ሶራ አዘነላት፡፡ ምን ሊያደርግላት እንደሚችል አሰበ፡፡
መላው አጥጋቢ አልመሰለውም፡፡ ይሻል ይሆናል ብሎ ገመተና ጮክ
በማለት ደግሞ ጠራት፡-
“ኮንችት…….” ሲል ሰማዩ ብልጭልጭ አለና የጆሮ
ታንቡራቸው የተነደለ እስኪመስል ብራቁ ጮኸ፡፡ሁለቱም በደመነፍስ ዝቅ አሉ በድንጋጤ፡፡
ኮንቺት አያቷ ትዝ አላት አደራው ተጭኗት ኖሯል፡፡
ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍላ አደራውን መፈፀም መቻል አለበት፡፡ህሊናዋ ከዚህ ግዴታዋ ውልፍት እንድትል አይፈቅድላትም፡፡ የዚያ ምስኪን ኢትዮጵያዊ አያቷን ዘመዶች ከመፈለግ ከአቅሟ በላይ በሆነ
ችግር ሞት ጥፍሩን አሽሎ መጣሁ' እያለ ቢያስፈራራትም እንኳ
ላለመሽሽ ለራሷ ቃል ገብታለች፡፡ ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ አስባ
ከማያዳግም ውሳኔ ላይ ደርሳለች፡፡
ብራቁ ካለፈ በኋላ ማጉረምረሙ እየበዛ የመጣውን ሰማይ ቀና ብሎ አየና ሶራ ኮንችትን አያት፡፡ ከዝያቡ ሊያድናት ፈለገ
ስለዚህ ጮክ ብሎ ጠራት
ኮንችት ለምን ጉዞውን አቁመን እንጠለልም፡፡ ከዚያ…" ብሎ ሃሣቡን ሳይጨርስ ገሃነም ግባ እሽ ቦቅቧቃ ፈሪ ነህ! ወደፈለግበት መሄድ
ትችላለህ! እኔን ግን አትጥራኝ ደደብ!" አለችው፡ ሶራ መብረቁ ጭንቅላቱ ላይ እንደወደቀ ሁሉ ክው አለ። ስላዘነላት ነበር የጠየቃት እሷ ግን አውሬ ሆነችበት ።
ሶራ እንደተወጋ አውሬ ሸቅሽቆት ውስጡ የገባው አነጋገሯ አደነዘዘው አበሸቀው።
ዝናቡ ህፃናት የሚጫወቱበትን ብይ እያካከለ ዥጉድጉድ
ብሎ መውረድ ጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ማየት እንኳ ተሳናቸው፡፡የመዋኛ መነፅራቸውን አደረጉ: ጉሙ እየሸፈነ ይበልጥ ማየት
ተሳናቸው፡ ቀስ እያለ ደግሞ አዙሪቱ ሰማያዊ ጀልባዋን ወደ ታች ሳይሆን እንባለሌ ያዞራት ጀመር፡፡
ሁለቱም ባለ ሃይላቸው ቀዘፉ አዙሪቱ ደግሞ እነሱን
ይበልጥ እያሽከረከረ ቀዘፋቸው፡፡ ቁልቁልና ሽቅቡ ዳሩና መሃሉ እስኪጠፋቸው ድረስ ከላይ ዝናቡ ከታች ዙሪቱ ልባቸውን
አጠፈው፡
ድንገት ደግሞ ዥው ብለው በአየር ላይ ሲንሳፈፉ እነሱ
ከሥር ጀልባዋና ውሃው ከላይ ሆኑ፡፡ ከሁሉም የከፋው አዲስ መከራ
ተጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ውሃው ያላጋቸዋል ያሰጥማቸዋል። ዝናቡ
ከላይ ዶፉን ያወርደዋል፡፡ ወገባቸው ላይ ገመዷን ያሰሯት ጀልባም
ወዲህ ወዲያ ትመነጭቃቸዋለች በጀልባዋ ወለል የነበረውን
ጓዛቸውንም ኦሞ ሰለቀጠው፡፡
ሰማዩ አልበቃውም ያጉረመርማል ይጮሃል፤
ይወርዳል. ኦሞ ወንዝም እርጋታው ጠፍቶ ይደነፋል ይሽከረከራል እላይ ደርሶ ይፈርጣል አሶች አዞዎችና ጉማሬዎች የሚሉትና
የሆኑት አይታወቅም፡፡ ኮንችትና ሶራ ግን አበሳቸውን ያያሉ። በኒያ
ወጣቶች መሃል ውሃ ገባ በቅጽበት እንደ ተራራ የገዘፈ ችግርና መከራ ላያቸው ላይ ተከመረ ይባስ ብሎ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አካባቢውን ፅልመት አለበሰው፡፡ ኮንችት መከራው ሲበዛባት ያመለጠች መስሏት የጀልባዋን ገመድ ከጎኗ ፈታችው፡፡ ከዚያ ከሶራና ከጀልባዋ ተጠፋፋች… እሪ ይላል ሰማዩ፡- አካባቢው
በእሮሮ በእግዚኦታ ተዋጠ፡፡
ሶራ ጀልባዋ እየጎተተችው ብዙ ከተጓዘ በኋላ በጭንቅ ወደ ዳር ወጣ፡፡ የይወት ማዳኛ ጃኬቱና ሄልሜቱ ነፍሱን አተረፋት፡ ዝናቡ ቆሟል ቀና ብሉ ሰማዩን አየ፡፡ ሰማዩ ጠርቷልı ጨረቃ ወጥታለች ከዋክብት ብልጭ ድርግም ይላሉ፡፡ ሶራ የሆነውን ሁሉ
ለማሰብ ሞከረ፡፡
ጀልባዋ ከሱ ጋር ነች፡፡ ኮንችት ግን አብራው የለችም፡ ያች መለሎዋ ያች ኢትዮጵያዊት ደፋርና የፍቅር ልዕልቱ አጠገቡ
የለችም፡፡ ከጀልባዋ ጋር ያያዘችው ገመድ ተበጥሷል፡፡
ሶራ ኦሞን ዞር ብሉ አየው፡፡
“ኦሞ አላማ ያለውን ሰው እውን ትበላለህ?” ብሎት ማልቀስ ጀመረ ሶራ። ጮኸ “ፍቅሬን ምሳሌዬን… ተነጠቅሁ” ብሎ ቀና
ብሎ ሰማዩን እያዬ ተማፀነ፡፡
እኔንም መብላት አለብህ ኦሞ፡፡ልትነጣጥለን አይገባም ሲሆን እኔን ማስቀደም ነበረብህ…” እየተንቀጠቀጠ አለቀሰ፡፡
“ምነው እግዚአብሔር... ምነው! የኦሞ ወንዝ ዳርን ጭቃ እያፈሰ ፊቱን እየቀባ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ለአምላኩ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ የሶስተኛ ቀን የኦሞ ወንዝ ላይ ጉዟቸውን
ሲጀምሩ አየሩ ጨፍገግ ያለና ሰማዩ በጥቁር ዳመናዎች የተሸፈነ
ነበር፡፡
“ብንቆይ አይሻልም ኮንችት"
“አይ! አስቸጋሪውን ጉዞ ብንጋፈጠው ይሻላል፡፡ ምናልባት እየተጓዝን ዝናቡን ልናመልጠው እንችል ይሆናል፡፡ስለዚህ ቶሉ
መንቀሳቀሳችን ይሻላል፡"
“ወንዙ ላይ ዝናቡ ከያዘንስ?''
“ያኔ ከወንዙ ወጥተን ድንኳን ወጥረን እንጠለላለን፤ እዚህ
ሆኖ ሳይሞክሩ ተሸናፊ መሆን ግን አልፈልግም" አለችው፡
“እሽ በኔ በኩል ለጉዞ ዝግጁ ነኝ፡፡"
“ቆየኝ አንዴ” ብላው ለመፀዳዳት ወደ ጫካው ገባች፡፡ ሶራ የወንዝ ላይ ጉዞ አስደሳችም አስፈሪም እንደሆነ እየተረዳ መጥቷል፡፡
በተለይ ከመጀመሪው ቀን ቀጥሎ በነበረው ውድቅት ሌሊት አንበሶች የድሪያ ወቅታቸ በመሆኑ ከድንኳናቸው ብዙም ሳይርቅ እያገሱ ሲታገሉ
ኮንችትና ሶራ ከአሁ አሁን ላያችን ላይ ወጡ ገነጣጥለው ሊቀራመቱን ነው ሲሉ እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር ነው ያደሩት።
በሁሉተኛው ቀን ደግሞ ድንገት የጣለው ከባድ ዝናብ ድንኳናቸውን በጎርፍ ውጦ ልብሳቸው በሙሉ ረጥቦ በዚያ ጥርስ
በሚፋጨው ብርድ እንደከበት ዛፍ ስር ጎን ለጎን ኵርም† ብለው
አንዱ በሌላው ትንፋሽ ሙቀት እየተጋሩ ነበር የመከራ ሌሊቱን ያሳለፉት።
ስለዚህ በነጋታው እስከ አጥንታችው ድረስ ዘልቆ የገባው ቆፈን እስኪወጣላቸው ፀይይ ላይ ተሰጥተው አረፈዱ ሰውነታቸውን ማዘዝና ማንቀሳቀስ ሲችሉ በጎርፍ የተዋጠውን ድንኳን ነቅለው
እቃውን አውጥተው… ፀሐይ ላይ አሰጡት ከዚያ ረጅም ሰዓት ቆይተው ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ተነስተው ሰላሳ ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንቅልፍና ድካም ተጫጭኖአችው ስለነበር ደረቅ ዳቦና ብስኩት ብቻ ተመግበው ተኙ ልክ እንደሞተ ሰው ተኝተው
አድረው ሲነቁ ስማዩ የታቀፈውን ጥላሽት የመሰለ ዳመና እላያችው
ላይ ሊዘረግፈው ተዘጋጅቷል።
የሶራ ምርጫ ዝናቡን ማሳለፍ ይሻላል ነበር ኮንችት ግን ሃሳቡን ልተቀበለችውም።
አሁን መሄድ እንችላለን የህይወት ማዳኛ ጃኬቱን ልበስ ሱሪውን አውልቀውና የዋና ፓንትህን ታጠቅ አለችው ሶራ የተባለውን እየፈፀመ አያት የለበሰችው የዋና ፓንቷን ነው
ጭኖችዋ ከምን ጊዜውም በላይ አምረዋል: ከላይ ቀይ የህይወት ማዳኛ ጃኬቷን ቀይ ሄልሜቷን ደፍታ ዮጉዞ ቦርሳን ከጀርባሞ አዝላለች ሶራም እንደ እሷ ትጥቁን እያስመረ ስማዩን ቀና ብሎ
አየው ጠቁሯል
ጀልባዋን ውሃው ላይ ካሳረፉ በኋላ ድንኳናቸው
ምግባቸውን የማብሰያ እቃቸውን… ከጀልባው መሀል አስቀምጠው
በጣም አስፈላጊ የሆነውን ቁሳቁስ በጀርባ ቦርሳቸው አዘሉት፡፡ ከዚያ “አድሪፍት" የምትለው ጀልባ ላይ ያለውን ረጅም ገመድ ወገባቸው ላይ ካለው ሰፊ ቀበቶ ጋር አያያዙት፡፡
ጀልባዋ ላይ ወጥተው ሚዛናቸውን ለመጠበቅ ከኋላ በኩል ግራና ቀኙ ተቀመጡና መቅዘፊያቸውን አንስተው አውራ ጣታቸውን
በማንሳት ዝግጁ ተባባሉና ወደ ኦሞ ወንዝ መሃል ሄደው ቁልቁል ቀዘፉ
ሰማዩ እንደ ተቆጣ ነብር ማጉረምረም ጀመረ። ድንገት ሰማዩ በቀጫጭን የብርሃን ዝግዛግ እየተሰነጣጠቀ ብልጭታው
ይታይና ብራቁ ድብልቅልቅ ብሎ መጮሁ እየጨመረ ሄደ፡፡
“ኮንችት!” ብሎ ጠርቶ አያት፡፡ ቶሎ ቶሎ ትቀዝፋለች ለማምለጥ፡፡ ድክም ያላት መሆኑ በዚያ ቆፈን የሚወርደው ላቧ ያስታውቃል፡፡ ሶራ አዘነላት፡፡ ምን ሊያደርግላት እንደሚችል አሰበ፡፡
መላው አጥጋቢ አልመሰለውም፡፡ ይሻል ይሆናል ብሎ ገመተና ጮክ
በማለት ደግሞ ጠራት፡-
“ኮንችት…….” ሲል ሰማዩ ብልጭልጭ አለና የጆሮ
ታንቡራቸው የተነደለ እስኪመስል ብራቁ ጮኸ፡፡ሁለቱም በደመነፍስ ዝቅ አሉ በድንጋጤ፡፡
ኮንቺት አያቷ ትዝ አላት አደራው ተጭኗት ኖሯል፡፡
ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍላ አደራውን መፈፀም መቻል አለበት፡፡ህሊናዋ ከዚህ ግዴታዋ ውልፍት እንድትል አይፈቅድላትም፡፡ የዚያ ምስኪን ኢትዮጵያዊ አያቷን ዘመዶች ከመፈለግ ከአቅሟ በላይ በሆነ
ችግር ሞት ጥፍሩን አሽሎ መጣሁ' እያለ ቢያስፈራራትም እንኳ
ላለመሽሽ ለራሷ ቃል ገብታለች፡፡ ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ አስባ
ከማያዳግም ውሳኔ ላይ ደርሳለች፡፡
ብራቁ ካለፈ በኋላ ማጉረምረሙ እየበዛ የመጣውን ሰማይ ቀና ብሎ አየና ሶራ ኮንችትን አያት፡፡ ከዝያቡ ሊያድናት ፈለገ
ስለዚህ ጮክ ብሎ ጠራት
ኮንችት ለምን ጉዞውን አቁመን እንጠለልም፡፡ ከዚያ…" ብሎ ሃሣቡን ሳይጨርስ ገሃነም ግባ እሽ ቦቅቧቃ ፈሪ ነህ! ወደፈለግበት መሄድ
ትችላለህ! እኔን ግን አትጥራኝ ደደብ!" አለችው፡ ሶራ መብረቁ ጭንቅላቱ ላይ እንደወደቀ ሁሉ ክው አለ። ስላዘነላት ነበር የጠየቃት እሷ ግን አውሬ ሆነችበት ።
ሶራ እንደተወጋ አውሬ ሸቅሽቆት ውስጡ የገባው አነጋገሯ አደነዘዘው አበሸቀው።
ዝናቡ ህፃናት የሚጫወቱበትን ብይ እያካከለ ዥጉድጉድ
ብሎ መውረድ ጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ማየት እንኳ ተሳናቸው፡፡የመዋኛ መነፅራቸውን አደረጉ: ጉሙ እየሸፈነ ይበልጥ ማየት
ተሳናቸው፡ ቀስ እያለ ደግሞ አዙሪቱ ሰማያዊ ጀልባዋን ወደ ታች ሳይሆን እንባለሌ ያዞራት ጀመር፡፡
ሁለቱም ባለ ሃይላቸው ቀዘፉ አዙሪቱ ደግሞ እነሱን
ይበልጥ እያሽከረከረ ቀዘፋቸው፡፡ ቁልቁልና ሽቅቡ ዳሩና መሃሉ እስኪጠፋቸው ድረስ ከላይ ዝናቡ ከታች ዙሪቱ ልባቸውን
አጠፈው፡
ድንገት ደግሞ ዥው ብለው በአየር ላይ ሲንሳፈፉ እነሱ
ከሥር ጀልባዋና ውሃው ከላይ ሆኑ፡፡ ከሁሉም የከፋው አዲስ መከራ
ተጀመረ፡፡ ኮንችትና ሶራ ውሃው ያላጋቸዋል ያሰጥማቸዋል። ዝናቡ
ከላይ ዶፉን ያወርደዋል፡፡ ወገባቸው ላይ ገመዷን ያሰሯት ጀልባም
ወዲህ ወዲያ ትመነጭቃቸዋለች በጀልባዋ ወለል የነበረውን
ጓዛቸውንም ኦሞ ሰለቀጠው፡፡
ሰማዩ አልበቃውም ያጉረመርማል ይጮሃል፤
ይወርዳል. ኦሞ ወንዝም እርጋታው ጠፍቶ ይደነፋል ይሽከረከራል እላይ ደርሶ ይፈርጣል አሶች አዞዎችና ጉማሬዎች የሚሉትና
የሆኑት አይታወቅም፡፡ ኮንችትና ሶራ ግን አበሳቸውን ያያሉ። በኒያ
ወጣቶች መሃል ውሃ ገባ በቅጽበት እንደ ተራራ የገዘፈ ችግርና መከራ ላያቸው ላይ ተከመረ ይባስ ብሎ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አካባቢውን ፅልመት አለበሰው፡፡ ኮንችት መከራው ሲበዛባት ያመለጠች መስሏት የጀልባዋን ገመድ ከጎኗ ፈታችው፡፡ ከዚያ ከሶራና ከጀልባዋ ተጠፋፋች… እሪ ይላል ሰማዩ፡- አካባቢው
በእሮሮ በእግዚኦታ ተዋጠ፡፡
ሶራ ጀልባዋ እየጎተተችው ብዙ ከተጓዘ በኋላ በጭንቅ ወደ ዳር ወጣ፡፡ የይወት ማዳኛ ጃኬቱና ሄልሜቱ ነፍሱን አተረፋት፡ ዝናቡ ቆሟል ቀና ብሉ ሰማዩን አየ፡፡ ሰማዩ ጠርቷልı ጨረቃ ወጥታለች ከዋክብት ብልጭ ድርግም ይላሉ፡፡ ሶራ የሆነውን ሁሉ
ለማሰብ ሞከረ፡፡
ጀልባዋ ከሱ ጋር ነች፡፡ ኮንችት ግን አብራው የለችም፡ ያች መለሎዋ ያች ኢትዮጵያዊት ደፋርና የፍቅር ልዕልቱ አጠገቡ
የለችም፡፡ ከጀልባዋ ጋር ያያዘችው ገመድ ተበጥሷል፡፡
ሶራ ኦሞን ዞር ብሉ አየው፡፡
“ኦሞ አላማ ያለውን ሰው እውን ትበላለህ?” ብሎት ማልቀስ ጀመረ ሶራ። ጮኸ “ፍቅሬን ምሳሌዬን… ተነጠቅሁ” ብሎ ቀና
ብሎ ሰማዩን እያዬ ተማፀነ፡፡
እኔንም መብላት አለብህ ኦሞ፡፡ልትነጣጥለን አይገባም ሲሆን እኔን ማስቀደም ነበረብህ…” እየተንቀጠቀጠ አለቀሰ፡፡
“ምነው እግዚአብሔር... ምነው! የኦሞ ወንዝ ዳርን ጭቃ እያፈሰ ፊቱን እየቀባ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ ለአምላኩ
👍16
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሶራ ሲያገኛት በጭቃ ልውስውስ ብላ ሰው አትመስልም። ጦርሷቿ ይፏጫሉ ሰውነቷ ይንቀጠቀጣል አካሏ የማታዝበት በድን ሆኗል። በጀርባው ያዘለውን ፈቶ በፕላስቲክ የተጠቀለለ ስሊፒግ ባግ አውጥቶ የበሰበሰና በጭቃ የተለወሰ ልብሷን አውልቆ ፎጣ አልብሶ ስሊፒግ ባግ ውስጥ እየጎተተ አስገባት።
በውርርድ ደረቅ ቦታ የለም ደለሉ በሙሉ ጨቅይቷል ውሃ ተኝቶበታል ስለዚህ ሶራ በቶሎ ከዚህ አካባቢ መራቅ እንዳለበት አምኖ ጀልባዋን ለማምጣት ሄደ።
ሶራ የፕላስቲክ ጀልባዋን በኦሞ ወንዝ ዳር ለዳር እየቀዘፈ ኮንችት ወዳለችበት ሄደ።ከጀልባዋ ወርዷ ወደኮንቺት ሲጠጋ አትሰማም። እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ወስዷታል።
የጀርባ ቦርሳቸውን ከጫነ በኋላ እሷን ጀርባው ላይ
አስተካክሎ በሰፊ ቀበቶ ከገላው ጋር አሰራትና የጀልባዋን ገመድ ፈቶ
ቀስ ብሎ ጀልባዋ ላይ ወጣ፡ hዚያ ጆልባዋ ወለል ላይ ትራስ አድርጎ
አጋደማትና ከጀልባዋ በስተኋላ እግሩን አንፈራጦ ቁጭ ካለ በኋላ መቅዘፍ ጀመረ"
ቀኑ ፀሐያማና ነፋሻማ ነው፡፡ ኮንችት ወዲያ ወዲህ ሳትል
ተንጋላለች፡ ሶራ ትንሽ ሲቀዝፍ ይቆይና ጆሮ'ውን ልቧ ላይ ይደቅናል። ከዚያ ተመልሶ ደግሞ ይቀዝፋል…
የሞላው የኦሞ ወንዝም ቁልቁል መግፋቱን እየረዳው እስከ ቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ድረስ ተጓዘ፡፡
ኮንችት በስፓኒሽ “ውኀ" ትለውና አንገቷን ቀና አድርጎ
ሰሰጣት ጎንጨት ታደርግና ትተኛለች፡ ርሃቡ ራሱ ሊጎዳት እንደሚችል ቢያምንም ጀልባዋን ሊያቆምበት የሚችል የተሻለ ቦታ በማጣቱ እግር ጉልበት እየጨመረለት ብዙ እንደተጓዘ ሜዳማ ደረቅ• ጨሌ ሣርና ጥላቸው ዘርፈፍ ያሉ ዛፎች ዘንድ ደረሰ፡፡ ቀስ ብሎ እየቀዘፈ ጀልባዋን ወደ ዳር አስጠጋና ኮንችትን እንዳይጫናት
ተጠንቅቆ በጀርባው አዘላትና ቀስ ብሎ
ቁጭ አለ፡፡ ጀልባዋ
ስለምትንቀሳቀስ ጀልባዋን እንደገና ወደዳር
ይበልጥ አስጠግቶ
እንደተቀመጠ ተንጠራርቶ ወንዙ ዳር ላይ ያለ የዋርካ ሥር ያዘ ያለው እድል ያ ብቻ ነበር።
መቅዘፊያውን ከጀልባዋ ላይ ፈቶ ወደ ውሃው ውስጥ ከቶ ለካው፡፡ መሬቱን ነክቶ ለመሻገር ኮንችትን አዝሉ እስከ አንገቱ ውሃ
ውስጥ መነከር አለበት፡፡ ምናልባት ከታች ያለው መሬት ድቡሽት
ከሆነ ስለሚሰምጥ እሷን ይዞ ለመዳን ይፍጨረጨር ይሆናል፡፡ እሷን አዝሎ ግን ካልተመቸው እንደተመኘው ሁለቱም እንደተዛዘሉ
አብረው ከአስቸጋሪው ሕይወት ለዘላለም ያርፋሉ፡፡ሶራ አሁን አልፈራም፡፡ ተለያይቶ ከመሞት አብሮ መሞትን ይመረጣል፡፡
በአርግጥ ሞትን ሊያመልጥ ብዙ ተጉዟል፡ ብዙ ሸሽቷል፡፡ ሞትን ግን ሊያመልጠው አልቻለም፡፡ ለሁሉም ወረቀት ፅፎ ሊያስቀምጥ ፈለገ፡ አዎ የሷም ሆኑ የእሱ ዘመዶች ሙት እንደሆናቸው መጠን እንደማንኛውም ሰው መሞታቸውን አውቀው ልሳቸውን በማውጣት በነሱ ላይ ያላቸው አጉል የተስፋ ህልማቸው ሊቆም ያስፈልጋል የእሱንም
የእሷንም ስም አድራሻ… ፃፈና በላስቲከ አስሮ ወገቡ ላይ ባሰረው ውሃ የማይገባው ላይነን ቀረጢት ከተተው፡፡
ከዚያ ውሃው ሲወስዳቸው እንዳይለያዩ በሌላ የዕቃ ማሰሪያ ቀበቶ በሷና እሱ ትከሻና ጉያ ስር አሰረው፡፡
“እፎይ ድሮ ሞትን እንዴት እፈራው ነበር፡፡ አሁን ግን
ቢያንስ መሞቴ እንደማይቀርልኝ አመንሁ! ከማንም ሰው በላይ
የመሞቻ ጊዜዬ መድረሱን ከነደቂቃው አውቄያለሁ, ከፍቅረኛ ጋር ደግሞ ወደ ሞት መሄዴ የሙት ዕድለኛ ያደርገኛል" ብሎ እዕዋቱን
ሰማዩን የማታዋን ጀንበር ከማህደሩ መግደያ ሰይፉን በመምዝ ላይ ያለውን የኦሞን ወንዝ አየና የዋርካ ስሩን ጠበቅ አድርጎ ይዞ
ከጀልባዋ ወደ ውሃው ውስጥ ገባ፡፡
የኢትዮጵያዊውን አያቷን እትብት የተቀበረበትን ለመፈለግ ደክማ ያልተሳካላትን ቆንጆ ውሃው ውስጥ እየገባ አያት፡፡ ከዚያ
ውሃው አሰመጠው? እንደፈራው ከደረቱ አላለፈም፡፡ ስለዚህ በዛፉ
ሥር አማካኝነት እየተጎተተ ወደ ውጭ ወጣ፡፡ መከራና ስቃይን ውጦ እንደጨረሰ ሁሉ ፊቱ በደስታ ፀዳል በራ፡ በቅፅበት ከመከራ
ወደ ደስታ ተመለሰ፡፡
ከዚያ ጫካ ውስጥ ገብቶ የደራረቁ እንጨቶችን ለቅሞ
አመጣና ውኃ የማያበላሸውን ክብሪት ጭሮ እሳት አቀጣጠለ፡፡
ከጀልባዋ ላይ ያለውን የጀርባ ሻንጣ አውርዶ ለኮንችት ፓንት ሣይቀር ቀይሮ እሳቱ ዳር አስተኛትና ለችግር ጊዜ ብለው የያዟትን
ትንሽ ድንኳን ዘረጋ፡፡
ከጀርባ ሻንጣው ተጣጣፊ መጥበሻና ብረት ድስት አውጥቶ ለችግር ጊዜ ካስቀመጡት ምግብ መካከል የሚበላ አዘጋጀና ሻይ አፈላ ኮንችት ቀስ በቀስ ዓይኖቿን መግለጥ ስትጀምር የአይብና አሳ ሳንዲዊች ወደ አፏ አስጠጋላት ከጭኖቹ ደገፍ እንዳለች ሳንዱቹን ገመጠች ሻየለንም መጠጣት ጀመረች።
ከዚያ የራስ ምታታ መድሃኒት እንደዋጠች ፈሳሽ ቅባት ጀርባዋን ጭኖቿን ክንዷን ፊቷን እያሸላት እቅልፍ ይዟት ሄደ ቀስ አድርጎ አቀፈና ድንኳን ውስጥ አስተኛት።
የሱ እስሊፒግ ባግ ካንጠለጠለበት ዛፍ ላይ ንፋሱ ሲያወዛውዘው ጠፈፍ እስኪልለት እሳቱ ዳር ጋደም አለና ሽቅብ ወደ ሰማይ አየ። ሰማዩ ጥርት ያለ ደመና አልባ ነው አየሩ በደንብ እንደበዘቀዘ እርጎ የሚገመጥ ነው ተወርዋሪ ኮኮቦች ይወረወራሉ ጨረቃ ትንሳፈፊለች ድንቁ ተፈጥሮ እንደገና የሚያስጓመጅ ሆኗል ቀናት ያልፋሉ ዛሬም አይቀርም ያልፋል ግን በሚያልፍ ጊዜ ስንቱ አዝኖ ስንቱ ይደሰታል?
እኩለ ሌሊት ላይ የትንሿ ድንኳን ዚፕ ጢዝዝዝ ብሎ ተከፈተ ጨለማው በጨረቃ ብርሃን ድል ተነስቷል የእሳቱ ነበልባል ጠፍቷል ፍሙ ግን አለ አጠገቡ ኩርምትምት ብሎ የተኛው ሶራ ነገር አለሙን ዘንግቶ እንቅለሰፉን ይለዋል።
ኮንቺት እጇን ግንባሩ ላይ አስቀመጠች ሶራ አልተንቀሳቀሰም ዝቅ ብላ አየችው። ተመልሳ ደግሞ የሆነውን ሁሉ ለማስታወስ ሞከረች ሰመመናዊ ህልሟ ሳይቀር።
ሶራ ከዚያ መአትና የጫካ አውሬ አፍ አውጥቷታል አሁን ግን ያሉበት ተፈጥሮ እየነፈሰ ስሜትን የሚኮረኩር ነው። እንደገና አየችው ሶራ የለበሰው ስሊፒግ ባግ እርጥብ በጭቃ የተለወሰ ነው።
ዝቅ ብላ ከንፈሩን ሳመችውና ቀና ብላ ላፈቅርህ በመቻሌ ደስታ ይሰማኛል አለችው እንደዚያ እንደ ዘቢብ የጣፈጠ አባባሏን ቢሰማ ኖሮ ምንኛ በደስታ በፈነጠዘ የተቃጠለ አንጀቱ እንዴት በራሰ ግን አልሰማትም መልካም ነገር እንዲህ በቀላሉ መቼ
ይሰማል!
ኮንችት ቀስ ብላ የሞቀ ትኩስ ትንፋሽዋን በጆሮ ግንዱ እያንቦለቦለች
“ሶራ ሶራ..." አለችውና ጭቃ የተቀባባውን አንገቱን
ግንባሩን ስትስመው አይኖቹን እንደምንም ብሎ ከፈተደ።
“ሶራ" ያ ሙዚቃዊ ጣዕም ያለው ድምፅ ጆሮው ላይ
አዜመ። ለመንቃት ታገለና አያት
ኮንችት! ጥርሱ ሳቀና አይኑ እንባ ሞልቶ ወደ ጎን ወደ
ጆሮ ግንዱ ፈሰሰ፡ ኮንችት እንባውን በምላሷ ቀመሰችው በፍቅር
የተቀመመ ጣፋጭ ነው እንባው!
“አፈቅርሃለሁ የእኔ ማር!'' አለችው። ሶራ አባባሏ
“አታፍቅሪኝ ኮንችት! ካፈቀርሽኝ ፍቅሬ ይከብድሻል ከከበደሽ ደግሞ ወርውረሽ ትጥይውና ትጠፊብኛለሽ:: ያኔ መከራ ይውጠኛል: ስለዚህ…" ከንፈሩን በከንፈሯ ከደነችው:: ከንፈሯ
ትንፋሽዋ ምላሷ. ሙቅ ነው።
ፍቅር ይከብደኛል!
ስፈራው ስሸሸው ኖሪያለሁ:
ካለፍቅር መሞት አልፈልግም የሞትን በር ሳንኳኳ+ የሚከፍቱት
ሲንቀራፈፉ አንተ ነጥቀህ መለስኸኝ። እኔ ደግሞ ፍቅሬን ዘንጥፌ
ልሰጥህ ወሰንኩ! ላለማፍቀር ስሸሽ እንደኖርኩት! ለማፍቀር ደግሞ ቅንጣት ታክል ፍርሃት የሌለኝ ደፋር ነኝ!
ሶራ ተምታታበት፤ ሳታፈቅረው እንዳፈቀራት አብሯት ቢዞር መከራም ገፍቶ ቢመጣ ቀድሟት ቢሞት ደስተኛ ነው።
ፍቅሯን እንደተሸከመው ሁሉ አሷም ፍቅሩን ብትሸከመው ሸክሟን ወርውራ ትሸሸው ይሆን?
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሶራ ሲያገኛት በጭቃ ልውስውስ ብላ ሰው አትመስልም። ጦርሷቿ ይፏጫሉ ሰውነቷ ይንቀጠቀጣል አካሏ የማታዝበት በድን ሆኗል። በጀርባው ያዘለውን ፈቶ በፕላስቲክ የተጠቀለለ ስሊፒግ ባግ አውጥቶ የበሰበሰና በጭቃ የተለወሰ ልብሷን አውልቆ ፎጣ አልብሶ ስሊፒግ ባግ ውስጥ እየጎተተ አስገባት።
በውርርድ ደረቅ ቦታ የለም ደለሉ በሙሉ ጨቅይቷል ውሃ ተኝቶበታል ስለዚህ ሶራ በቶሎ ከዚህ አካባቢ መራቅ እንዳለበት አምኖ ጀልባዋን ለማምጣት ሄደ።
ሶራ የፕላስቲክ ጀልባዋን በኦሞ ወንዝ ዳር ለዳር እየቀዘፈ ኮንችት ወዳለችበት ሄደ።ከጀልባዋ ወርዷ ወደኮንቺት ሲጠጋ አትሰማም። እንቅልፍ ጭልጥ አድርጎ ወስዷታል።
የጀርባ ቦርሳቸውን ከጫነ በኋላ እሷን ጀርባው ላይ
አስተካክሎ በሰፊ ቀበቶ ከገላው ጋር አሰራትና የጀልባዋን ገመድ ፈቶ
ቀስ ብሎ ጀልባዋ ላይ ወጣ፡ hዚያ ጆልባዋ ወለል ላይ ትራስ አድርጎ
አጋደማትና ከጀልባዋ በስተኋላ እግሩን አንፈራጦ ቁጭ ካለ በኋላ መቅዘፍ ጀመረ"
ቀኑ ፀሐያማና ነፋሻማ ነው፡፡ ኮንችት ወዲያ ወዲህ ሳትል
ተንጋላለች፡ ሶራ ትንሽ ሲቀዝፍ ይቆይና ጆሮ'ውን ልቧ ላይ ይደቅናል። ከዚያ ተመልሶ ደግሞ ይቀዝፋል…
የሞላው የኦሞ ወንዝም ቁልቁል መግፋቱን እየረዳው እስከ ቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ድረስ ተጓዘ፡፡
ኮንችት በስፓኒሽ “ውኀ" ትለውና አንገቷን ቀና አድርጎ
ሰሰጣት ጎንጨት ታደርግና ትተኛለች፡ ርሃቡ ራሱ ሊጎዳት እንደሚችል ቢያምንም ጀልባዋን ሊያቆምበት የሚችል የተሻለ ቦታ በማጣቱ እግር ጉልበት እየጨመረለት ብዙ እንደተጓዘ ሜዳማ ደረቅ• ጨሌ ሣርና ጥላቸው ዘርፈፍ ያሉ ዛፎች ዘንድ ደረሰ፡፡ ቀስ ብሎ እየቀዘፈ ጀልባዋን ወደ ዳር አስጠጋና ኮንችትን እንዳይጫናት
ተጠንቅቆ በጀርባው አዘላትና ቀስ ብሎ
ቁጭ አለ፡፡ ጀልባዋ
ስለምትንቀሳቀስ ጀልባዋን እንደገና ወደዳር
ይበልጥ አስጠግቶ
እንደተቀመጠ ተንጠራርቶ ወንዙ ዳር ላይ ያለ የዋርካ ሥር ያዘ ያለው እድል ያ ብቻ ነበር።
መቅዘፊያውን ከጀልባዋ ላይ ፈቶ ወደ ውሃው ውስጥ ከቶ ለካው፡፡ መሬቱን ነክቶ ለመሻገር ኮንችትን አዝሉ እስከ አንገቱ ውሃ
ውስጥ መነከር አለበት፡፡ ምናልባት ከታች ያለው መሬት ድቡሽት
ከሆነ ስለሚሰምጥ እሷን ይዞ ለመዳን ይፍጨረጨር ይሆናል፡፡ እሷን አዝሎ ግን ካልተመቸው እንደተመኘው ሁለቱም እንደተዛዘሉ
አብረው ከአስቸጋሪው ሕይወት ለዘላለም ያርፋሉ፡፡ሶራ አሁን አልፈራም፡፡ ተለያይቶ ከመሞት አብሮ መሞትን ይመረጣል፡፡
በአርግጥ ሞትን ሊያመልጥ ብዙ ተጉዟል፡ ብዙ ሸሽቷል፡፡ ሞትን ግን ሊያመልጠው አልቻለም፡፡ ለሁሉም ወረቀት ፅፎ ሊያስቀምጥ ፈለገ፡ አዎ የሷም ሆኑ የእሱ ዘመዶች ሙት እንደሆናቸው መጠን እንደማንኛውም ሰው መሞታቸውን አውቀው ልሳቸውን በማውጣት በነሱ ላይ ያላቸው አጉል የተስፋ ህልማቸው ሊቆም ያስፈልጋል የእሱንም
የእሷንም ስም አድራሻ… ፃፈና በላስቲከ አስሮ ወገቡ ላይ ባሰረው ውሃ የማይገባው ላይነን ቀረጢት ከተተው፡፡
ከዚያ ውሃው ሲወስዳቸው እንዳይለያዩ በሌላ የዕቃ ማሰሪያ ቀበቶ በሷና እሱ ትከሻና ጉያ ስር አሰረው፡፡
“እፎይ ድሮ ሞትን እንዴት እፈራው ነበር፡፡ አሁን ግን
ቢያንስ መሞቴ እንደማይቀርልኝ አመንሁ! ከማንም ሰው በላይ
የመሞቻ ጊዜዬ መድረሱን ከነደቂቃው አውቄያለሁ, ከፍቅረኛ ጋር ደግሞ ወደ ሞት መሄዴ የሙት ዕድለኛ ያደርገኛል" ብሎ እዕዋቱን
ሰማዩን የማታዋን ጀንበር ከማህደሩ መግደያ ሰይፉን በመምዝ ላይ ያለውን የኦሞን ወንዝ አየና የዋርካ ስሩን ጠበቅ አድርጎ ይዞ
ከጀልባዋ ወደ ውሃው ውስጥ ገባ፡፡
የኢትዮጵያዊውን አያቷን እትብት የተቀበረበትን ለመፈለግ ደክማ ያልተሳካላትን ቆንጆ ውሃው ውስጥ እየገባ አያት፡፡ ከዚያ
ውሃው አሰመጠው? እንደፈራው ከደረቱ አላለፈም፡፡ ስለዚህ በዛፉ
ሥር አማካኝነት እየተጎተተ ወደ ውጭ ወጣ፡፡ መከራና ስቃይን ውጦ እንደጨረሰ ሁሉ ፊቱ በደስታ ፀዳል በራ፡ በቅፅበት ከመከራ
ወደ ደስታ ተመለሰ፡፡
ከዚያ ጫካ ውስጥ ገብቶ የደራረቁ እንጨቶችን ለቅሞ
አመጣና ውኃ የማያበላሸውን ክብሪት ጭሮ እሳት አቀጣጠለ፡፡
ከጀልባዋ ላይ ያለውን የጀርባ ሻንጣ አውርዶ ለኮንችት ፓንት ሣይቀር ቀይሮ እሳቱ ዳር አስተኛትና ለችግር ጊዜ ብለው የያዟትን
ትንሽ ድንኳን ዘረጋ፡፡
ከጀርባ ሻንጣው ተጣጣፊ መጥበሻና ብረት ድስት አውጥቶ ለችግር ጊዜ ካስቀመጡት ምግብ መካከል የሚበላ አዘጋጀና ሻይ አፈላ ኮንችት ቀስ በቀስ ዓይኖቿን መግለጥ ስትጀምር የአይብና አሳ ሳንዲዊች ወደ አፏ አስጠጋላት ከጭኖቹ ደገፍ እንዳለች ሳንዱቹን ገመጠች ሻየለንም መጠጣት ጀመረች።
ከዚያ የራስ ምታታ መድሃኒት እንደዋጠች ፈሳሽ ቅባት ጀርባዋን ጭኖቿን ክንዷን ፊቷን እያሸላት እቅልፍ ይዟት ሄደ ቀስ አድርጎ አቀፈና ድንኳን ውስጥ አስተኛት።
የሱ እስሊፒግ ባግ ካንጠለጠለበት ዛፍ ላይ ንፋሱ ሲያወዛውዘው ጠፈፍ እስኪልለት እሳቱ ዳር ጋደም አለና ሽቅብ ወደ ሰማይ አየ። ሰማዩ ጥርት ያለ ደመና አልባ ነው አየሩ በደንብ እንደበዘቀዘ እርጎ የሚገመጥ ነው ተወርዋሪ ኮኮቦች ይወረወራሉ ጨረቃ ትንሳፈፊለች ድንቁ ተፈጥሮ እንደገና የሚያስጓመጅ ሆኗል ቀናት ያልፋሉ ዛሬም አይቀርም ያልፋል ግን በሚያልፍ ጊዜ ስንቱ አዝኖ ስንቱ ይደሰታል?
እኩለ ሌሊት ላይ የትንሿ ድንኳን ዚፕ ጢዝዝዝ ብሎ ተከፈተ ጨለማው በጨረቃ ብርሃን ድል ተነስቷል የእሳቱ ነበልባል ጠፍቷል ፍሙ ግን አለ አጠገቡ ኩርምትምት ብሎ የተኛው ሶራ ነገር አለሙን ዘንግቶ እንቅለሰፉን ይለዋል።
ኮንቺት እጇን ግንባሩ ላይ አስቀመጠች ሶራ አልተንቀሳቀሰም ዝቅ ብላ አየችው። ተመልሳ ደግሞ የሆነውን ሁሉ ለማስታወስ ሞከረች ሰመመናዊ ህልሟ ሳይቀር።
ሶራ ከዚያ መአትና የጫካ አውሬ አፍ አውጥቷታል አሁን ግን ያሉበት ተፈጥሮ እየነፈሰ ስሜትን የሚኮረኩር ነው። እንደገና አየችው ሶራ የለበሰው ስሊፒግ ባግ እርጥብ በጭቃ የተለወሰ ነው።
ዝቅ ብላ ከንፈሩን ሳመችውና ቀና ብላ ላፈቅርህ በመቻሌ ደስታ ይሰማኛል አለችው እንደዚያ እንደ ዘቢብ የጣፈጠ አባባሏን ቢሰማ ኖሮ ምንኛ በደስታ በፈነጠዘ የተቃጠለ አንጀቱ እንዴት በራሰ ግን አልሰማትም መልካም ነገር እንዲህ በቀላሉ መቼ
ይሰማል!
ኮንችት ቀስ ብላ የሞቀ ትኩስ ትንፋሽዋን በጆሮ ግንዱ እያንቦለቦለች
“ሶራ ሶራ..." አለችውና ጭቃ የተቀባባውን አንገቱን
ግንባሩን ስትስመው አይኖቹን እንደምንም ብሎ ከፈተደ።
“ሶራ" ያ ሙዚቃዊ ጣዕም ያለው ድምፅ ጆሮው ላይ
አዜመ። ለመንቃት ታገለና አያት
ኮንችት! ጥርሱ ሳቀና አይኑ እንባ ሞልቶ ወደ ጎን ወደ
ጆሮ ግንዱ ፈሰሰ፡ ኮንችት እንባውን በምላሷ ቀመሰችው በፍቅር
የተቀመመ ጣፋጭ ነው እንባው!
“አፈቅርሃለሁ የእኔ ማር!'' አለችው። ሶራ አባባሏ
“አታፍቅሪኝ ኮንችት! ካፈቀርሽኝ ፍቅሬ ይከብድሻል ከከበደሽ ደግሞ ወርውረሽ ትጥይውና ትጠፊብኛለሽ:: ያኔ መከራ ይውጠኛል: ስለዚህ…" ከንፈሩን በከንፈሯ ከደነችው:: ከንፈሯ
ትንፋሽዋ ምላሷ. ሙቅ ነው።
ፍቅር ይከብደኛል!
ስፈራው ስሸሸው ኖሪያለሁ:
ካለፍቅር መሞት አልፈልግም የሞትን በር ሳንኳኳ+ የሚከፍቱት
ሲንቀራፈፉ አንተ ነጥቀህ መለስኸኝ። እኔ ደግሞ ፍቅሬን ዘንጥፌ
ልሰጥህ ወሰንኩ! ላለማፍቀር ስሸሽ እንደኖርኩት! ለማፍቀር ደግሞ ቅንጣት ታክል ፍርሃት የሌለኝ ደፋር ነኝ!
ሶራ ተምታታበት፤ ሳታፈቅረው እንዳፈቀራት አብሯት ቢዞር መከራም ገፍቶ ቢመጣ ቀድሟት ቢሞት ደስተኛ ነው።
ፍቅሯን እንደተሸከመው ሁሉ አሷም ፍቅሩን ብትሸከመው ሸክሟን ወርውራ ትሸሸው ይሆን?
👍34❤2😱1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
የሐመር ታዋቂ ሽማግሌዎች ጫማ ጣዮች አንጀት አንባቢዎች... ቡስካ ላይ እንደገና ተሰባስበው ሸፈሮ ቡና ተፈልቶ
የጋራ ምርቃቱ ተዥጎደጎደ።
ጫማ ጣዮች ደልቲ ገልዲ ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ
ጫማቸውን እያሽከረከሩ እየወረወሩ የጫማውን አወዳደቅ ደጋግመው አዩና “ሰላም ነው፤ ወደ ኦሞ አቅጣጫ ሄዷል" አሉ፡
"አንጀት አንባቢዎች ደግሞ ትንበያቸውን ለመጀመር ሁለት ፍየሎችን አሳረዱና አንጀቱን በጥንቃቄ አነበቡት ! “አደጋ
አልደረሰበትም ሆዱ ውስጥ ግን ነገር አለ! መንገድ አሁንም እየተጓዘ ነው ወደ ፀሐይ መውደቂያ'' አሉ።
የፍየሎች ሥጋ በሐመር ደንብ መሰረት ወጠሌ ጥብስ ተጠበሰ፡ እሳቱ ከመሐል ነደደ የሥጋው ብልቶች ጫፉ በሾለ
ረጃጅም ችካል ላይ ተሰክቶ ችካሉ በሳቱ ዙሪያ ተተከለ: እሳቱ ሥጋውን አይነካውም፤ የእሳቱ ወላፈን ግን ሥጋውን ሙክክ አድርጎ አበሰለው።
ሽማግሌዎች የግማሽ ጨረቃ ክብ ሰርተው እንደ
እድሜያቸው ልዩነት ተቀመጡ። ከዚያ በሐመር ደንብ መሰረት የፍየሎቹ ፍሪንባ ለሽማግሌዎች ቀሪው ደግሞ ብልቱ እየተቆራረጠ እንደየ እድሜው ታደለ።
ሽማግሌዎች ሲመገቡ ጎረምሶችና ልጃገረዶች ራቅ ብለው ቁጭ አሉ። ከልጃገረዶች ውስጥ እንግሊዛዊቷ የስነ ሰብዕ ተመራማሪ አለች: ተመራማሪነቷ የሚያውቁት የማንቸስተር ዩንቨርስቲና ከሎ ሆራ ብቻ ናቸው፡ ሐመር ላይ ካርለት አንድ የሐመር ልጃገረድ ናት። የተገረፈችውን የጀርባ ላይ ምልክት ሳትሸፍን የፍየል ቆዳዋን ለብሳ ጭኖችዋን ጡቷን ለጎረምሶች እይታ ገልጣ ፀጉሯን አኖ
ተቀበታ ከሐመር ልጃገረዶች ጋር ወሬዋን እየሰለቀች የአባቷን
የሐመር ቀዩ በሣቋ የምታደምቅ ዝናብ ናት።
ካለ ዝናብ ጨሌ ሳር ካለ ጨሌ ሳር ከብት ካለ ከብት
ደግሞ ሐመሮች መኖር እንደማይችሉት ሁሉ በጨሌ በዛጎልና
በአምባር ያጌጡ ልጃገረዶች በሐመር ምድር ካልታዩ ሳቃቸጡ ካልተሰማ ዳንኪራቸው ካልታዬ... ሐመሮች የሉም ማለት ነው:
ካርለት አልፈርድ ከልጃገረዶች ጋር ሽማግሌዎች የሚፈፅሙትን ከቅርብ ሆና ታያለች: ጎይቲ መንደር ውስጥ ናት ከሎ ሆራ ግን የሐመር ደን (ያገባ ሙሉ ወንድ) በመሆኑ
ከሽማግሌዎች ግርጌ የተሰጠውን ያላምጣል።
ስነ-ስርዓቱ ካለቀ በኋላ ደልቲን ለመፈለጉ ከሎ ሆራና አንተነ ይመር ተመረጡና ተመርቀው አደራቸውን ከተቀበሉ በኋላ
ወደ ካርለት ሄዱ።
"መሄድ እንችላለን ካርለት"
"ምን ተባለ?”
"
“ያው እንዳየሽው ባህላዊ ትንበያው ተፈጽሟል። ወንዙን ከመሻገሩ በፊት ድረሱበት… ብለውናል" አላት።
hዚያ ተያይዘው ወደ መንደር ሄዱና ጎይቲን አገኝዋት የተባለውን ካርለት አስረዳቻት
“ጎይቲ ለብቻሽ ላናግርሽ?”
“ይእ! እሽ ምን አዲስ ነገር ገጠመሽ?"
ይኸውልሽ አሁን እንግዲህ ለፍለጋ መሄዳችን ነው::አንች
“ይእ ካርለቴ እኔ ልቀር ማለት ነው?
"አዎ አንቺ ቅሪ ከሎም ሊከፋው ይችላል አየሽ
እሱ .. "
“በይ በቃሽ እቴ አንችስ አንደኔ ሴት አደለሽ: የወለድሽው ልጅ አድጎ መልሶ አያገባሽ ግን ለምን ነው የምተወጂው
ለምን ነው ለልጅሽ
የምትሳሽው እኔ በርግጥ አግብችለሁ ግን
ያልወለድሁት ሽል ሆኖ ልቤ ውስጥ የሚኖር ሰው አለኝ ሆዴ ውስጥ ሲንከላወስ የማየው . ያ ሰው ልቤን በፍቅር መዳፍ መሃል
የያዘው በገዛ ፍላጎቴ ነበር ልቤን ከፍቼለፈት ውስጤ ገባ.. አሁን ያ ሰው ሲጠፋ ከማንም በላይ በሐዘን አንጀቱ የተመተረ ከኔ በላይ
ማንም የለም:: የፍቅር ጀግናዩ ልቤ ውስጥ የታቀፍሁትም ልጄ
ነው አውጥቼ የማልጥለው
“ይእ! እኔኮ ከንግዲህ ከእሱ ጋር የመቃበጥ እድሌ እንደ
እትብት ተቆርጧል እትብት ከመቼ ወዲህ ተመልሶ ተቀጥሎ ያውቃል ውስጤ የታቀፍኩት ግን ከገላዬ ጋር እንደተጣበቀ ነው ለልጄ ለፍቅሬ ጌታ እሳሳ እጨነቅለታለሁ ስለዚህ የሱን መጨረሻ ሳላውቅ ጎኔ አያርፍም! ልቤ አይተኛም::
እና የኔ እህት እባክሽ ሴት ሆነሽ የሴትነት ምጥ
ይሰማሽ" ብላ እንባዋን
ታወርደው ጀመር።
ሰውነቴ አረ ተይ ይብቃሽ አይንሽ ይጠፋል ምን
ይሆናል ብለሽ እንዲህ ቀን ከሌት የምታነቢው?
“ይእ ካርለትም ከሎም ደብቂው ዋሾ ሁኚ አንጀትሽ
እየከሰለ ሳቂ በእዝነ ልቦናሽ እያየሽው በአካል ግን አ
እጥፍጥፍ ብለሽ ተቀመጭ! ፍቅርሽን አውጠሽ ድፊው እያሉ ሲታከኩብኝ አታይም
ስቅ ስቅ ብላ አለቀሰች እንደገና::
"ተዋት የኔ ልጆች
የልጅነት ጨዋታዋን ዘንጊው ማለትማ ደግ አይደለም ማንስ የልጅነት ዘመኑን ዘንግቶት ያውቃል ምስጥ አለ አንተነህ ይመር: ወደ ልጅነት ዘመኑ
የኋልዮሽ እየተንደረደረ:: አየው የልጅነት ዘመን
ቡርቃውን…
“ሁሉ ነገር ሲለዋወጥ ካለበት የማይንቀሳቀስ ትዝታ ነው የልጅነት ዘመን! የወጣትነት ዘመን" ብሎ አንተነህ ይመር እንደ
ልጁ እሱም ወደ ልጅነት ትዝታው የኋልዮሽ ሮጠ ሁሉ
የሚጣፍጥበት ዘመን በራስ መተማመን ጢቅ ብሎ ሞልቶ የሚኮፈስበት ዘመን ትዝ አለው:
ተዋት አትፍረድባት አፍኝው ቻይው ምጥሽን አትናገሪ
አትበሏት ብሶቷን ታውጣው: ሐዘኗን ትግለፀው። እንዲህ ሁናስ መቼ ሰላም ይኖራታል አብራን ትሃድ፤ ተነሽ መስታዋቴ ከለ። ካርለት በተናገረችው ተፀፀተች: አንተነህ ሲናገር ህሊናዋን ሐዘን እንደቁርጥማት አኘካት። መኪናዋ አራቱን ፈላጊዎች ይዛ ወደ ኦሞ
ተንቀሳቀሰች።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወንዝ ላይ ጉዞውን ከጀመሩ ስምንት ቀን ሞላቸው። ወገቧ ላይ ቢጫ መስመር የተሰመረባት ሰማያዊ ጀልባ በኦሞ ወንዝ ላይ እየተንሳፈፈች ኩዱማ እና ማርኩል መንደሮች አደረሰቻቸው
ኮንችት አያቷ ባስጠናት መረጃ መሰረት በየመንደሩ
እየተዘዋወረች ስታስተውል አያቷ የነገራትን ፍንጭ ባለማግኘቷ ጎዞአቸውን ቀጠሉ።
ሙርሲ ማህበረሰብ ሲደርሱ ወንዶች ፀጉር
የማይወዱ የራስ ፀጉራቸውን የወንድ ብልታቸውን ብብታቸውን
የሚላጩና ፀጉር ማሳደግ እንደ ነውር የሚቆጠርበት
የወንዱን የራሱንም ሆነ የጉያውን ፀጉር መላጨት ያለባት ሴቷ መሆኗንና
ፀጉር ቢያድግ ግን የምትወቀስ ሴቷ እንደምትሆን አዩ።
የሙርሲ ሴቶች ከሸክላ አፈር የተሰራ ክብ ገል ኸንፈራቸው ላይ ጠፍጣፋ እንጨት ጆሮአቸው ላይ ያንጠለጥላሉ: ቁጥሩ
ከአምስት ሺ የማይበልጠው የሙርሲ ማህበረሰብ የተሻለ የግጦሽ ፈና የእርሻ ቦታ በመፈለግ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወር ከበርካታ አጎራባቾቹ ጋር በዚሁ የተሻለ ቦታ ለማግኘት ሲንቀሳቀስ የሚጠቃ ማህበረሰብ በመሆኑ በጥንቱ ዘመን ብዙውን ጊዜ የሙርሲ ሴቶች፡ ከብቶቹ
በግጭቱ ወቅት የሚዘርፍና ከሱዳን የሚመጡ ባርያ ፈንጋዮችም ሴቶቹን ስለሚወስዱባቸው ለዚያ መከላከያ የሙርሲ ሴቶች ከሌሎች ሴቶች የተለዩ እንዲሆኑ ገል ከንፈራቸው ላይ እንዲያስገቡ በማድረግ
የሴቶችን ዝርፊያ ማስቆሙ! ይኸ ጠቃሚ ዘዴ በማህበረሰቡ እንዲ
ለመድም ሰፋ ያለ ገል ከንፈራቸው ላይ የሰኩ ልጃገረዶች አነስ ያለ
ገል ካደረጉት ልጃገረዶች የበለጠ ጥሉሽ እንዲከፈልባቸው መደረጉ!
ያ ድርጊት ሴቶች በከንፈራቸውና ጆሮአቸው ገል እንዲሰኩ የተጀመ
ረው ተቀባይነት አግኝቶ እንዲቀጥል አሁን አሁን እንዲያውም ሰፊ
ገል hንፈር ላይ መሰካት ብዙ ጥሉሽ የሚያስገኝ በመሆኑ የቁንጅና
መለኪያ ተደርጎ በውጩ ማህበረሰብ እንደሚገመትም አወቁ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
የሐመር ታዋቂ ሽማግሌዎች ጫማ ጣዮች አንጀት አንባቢዎች... ቡስካ ላይ እንደገና ተሰባስበው ሸፈሮ ቡና ተፈልቶ
የጋራ ምርቃቱ ተዥጎደጎደ።
ጫማ ጣዮች ደልቲ ገልዲ ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ
ጫማቸውን እያሽከረከሩ እየወረወሩ የጫማውን አወዳደቅ ደጋግመው አዩና “ሰላም ነው፤ ወደ ኦሞ አቅጣጫ ሄዷል" አሉ፡
"አንጀት አንባቢዎች ደግሞ ትንበያቸውን ለመጀመር ሁለት ፍየሎችን አሳረዱና አንጀቱን በጥንቃቄ አነበቡት ! “አደጋ
አልደረሰበትም ሆዱ ውስጥ ግን ነገር አለ! መንገድ አሁንም እየተጓዘ ነው ወደ ፀሐይ መውደቂያ'' አሉ።
የፍየሎች ሥጋ በሐመር ደንብ መሰረት ወጠሌ ጥብስ ተጠበሰ፡ እሳቱ ከመሐል ነደደ የሥጋው ብልቶች ጫፉ በሾለ
ረጃጅም ችካል ላይ ተሰክቶ ችካሉ በሳቱ ዙሪያ ተተከለ: እሳቱ ሥጋውን አይነካውም፤ የእሳቱ ወላፈን ግን ሥጋውን ሙክክ አድርጎ አበሰለው።
ሽማግሌዎች የግማሽ ጨረቃ ክብ ሰርተው እንደ
እድሜያቸው ልዩነት ተቀመጡ። ከዚያ በሐመር ደንብ መሰረት የፍየሎቹ ፍሪንባ ለሽማግሌዎች ቀሪው ደግሞ ብልቱ እየተቆራረጠ እንደየ እድሜው ታደለ።
ሽማግሌዎች ሲመገቡ ጎረምሶችና ልጃገረዶች ራቅ ብለው ቁጭ አሉ። ከልጃገረዶች ውስጥ እንግሊዛዊቷ የስነ ሰብዕ ተመራማሪ አለች: ተመራማሪነቷ የሚያውቁት የማንቸስተር ዩንቨርስቲና ከሎ ሆራ ብቻ ናቸው፡ ሐመር ላይ ካርለት አንድ የሐመር ልጃገረድ ናት። የተገረፈችውን የጀርባ ላይ ምልክት ሳትሸፍን የፍየል ቆዳዋን ለብሳ ጭኖችዋን ጡቷን ለጎረምሶች እይታ ገልጣ ፀጉሯን አኖ
ተቀበታ ከሐመር ልጃገረዶች ጋር ወሬዋን እየሰለቀች የአባቷን
የሐመር ቀዩ በሣቋ የምታደምቅ ዝናብ ናት።
ካለ ዝናብ ጨሌ ሳር ካለ ጨሌ ሳር ከብት ካለ ከብት
ደግሞ ሐመሮች መኖር እንደማይችሉት ሁሉ በጨሌ በዛጎልና
በአምባር ያጌጡ ልጃገረዶች በሐመር ምድር ካልታዩ ሳቃቸጡ ካልተሰማ ዳንኪራቸው ካልታዬ... ሐመሮች የሉም ማለት ነው:
ካርለት አልፈርድ ከልጃገረዶች ጋር ሽማግሌዎች የሚፈፅሙትን ከቅርብ ሆና ታያለች: ጎይቲ መንደር ውስጥ ናት ከሎ ሆራ ግን የሐመር ደን (ያገባ ሙሉ ወንድ) በመሆኑ
ከሽማግሌዎች ግርጌ የተሰጠውን ያላምጣል።
ስነ-ስርዓቱ ካለቀ በኋላ ደልቲን ለመፈለጉ ከሎ ሆራና አንተነ ይመር ተመረጡና ተመርቀው አደራቸውን ከተቀበሉ በኋላ
ወደ ካርለት ሄዱ።
"መሄድ እንችላለን ካርለት"
"ምን ተባለ?”
"
“ያው እንዳየሽው ባህላዊ ትንበያው ተፈጽሟል። ወንዙን ከመሻገሩ በፊት ድረሱበት… ብለውናል" አላት።
hዚያ ተያይዘው ወደ መንደር ሄዱና ጎይቲን አገኝዋት የተባለውን ካርለት አስረዳቻት
“ጎይቲ ለብቻሽ ላናግርሽ?”
“ይእ! እሽ ምን አዲስ ነገር ገጠመሽ?"
ይኸውልሽ አሁን እንግዲህ ለፍለጋ መሄዳችን ነው::አንች
“ይእ ካርለቴ እኔ ልቀር ማለት ነው?
"አዎ አንቺ ቅሪ ከሎም ሊከፋው ይችላል አየሽ
እሱ .. "
“በይ በቃሽ እቴ አንችስ አንደኔ ሴት አደለሽ: የወለድሽው ልጅ አድጎ መልሶ አያገባሽ ግን ለምን ነው የምተወጂው
ለምን ነው ለልጅሽ
የምትሳሽው እኔ በርግጥ አግብችለሁ ግን
ያልወለድሁት ሽል ሆኖ ልቤ ውስጥ የሚኖር ሰው አለኝ ሆዴ ውስጥ ሲንከላወስ የማየው . ያ ሰው ልቤን በፍቅር መዳፍ መሃል
የያዘው በገዛ ፍላጎቴ ነበር ልቤን ከፍቼለፈት ውስጤ ገባ.. አሁን ያ ሰው ሲጠፋ ከማንም በላይ በሐዘን አንጀቱ የተመተረ ከኔ በላይ
ማንም የለም:: የፍቅር ጀግናዩ ልቤ ውስጥ የታቀፍሁትም ልጄ
ነው አውጥቼ የማልጥለው
“ይእ! እኔኮ ከንግዲህ ከእሱ ጋር የመቃበጥ እድሌ እንደ
እትብት ተቆርጧል እትብት ከመቼ ወዲህ ተመልሶ ተቀጥሎ ያውቃል ውስጤ የታቀፍኩት ግን ከገላዬ ጋር እንደተጣበቀ ነው ለልጄ ለፍቅሬ ጌታ እሳሳ እጨነቅለታለሁ ስለዚህ የሱን መጨረሻ ሳላውቅ ጎኔ አያርፍም! ልቤ አይተኛም::
እና የኔ እህት እባክሽ ሴት ሆነሽ የሴትነት ምጥ
ይሰማሽ" ብላ እንባዋን
ታወርደው ጀመር።
ሰውነቴ አረ ተይ ይብቃሽ አይንሽ ይጠፋል ምን
ይሆናል ብለሽ እንዲህ ቀን ከሌት የምታነቢው?
“ይእ ካርለትም ከሎም ደብቂው ዋሾ ሁኚ አንጀትሽ
እየከሰለ ሳቂ በእዝነ ልቦናሽ እያየሽው በአካል ግን አ
እጥፍጥፍ ብለሽ ተቀመጭ! ፍቅርሽን አውጠሽ ድፊው እያሉ ሲታከኩብኝ አታይም
ስቅ ስቅ ብላ አለቀሰች እንደገና::
"ተዋት የኔ ልጆች
የልጅነት ጨዋታዋን ዘንጊው ማለትማ ደግ አይደለም ማንስ የልጅነት ዘመኑን ዘንግቶት ያውቃል ምስጥ አለ አንተነህ ይመር: ወደ ልጅነት ዘመኑ
የኋልዮሽ እየተንደረደረ:: አየው የልጅነት ዘመን
ቡርቃውን…
“ሁሉ ነገር ሲለዋወጥ ካለበት የማይንቀሳቀስ ትዝታ ነው የልጅነት ዘመን! የወጣትነት ዘመን" ብሎ አንተነህ ይመር እንደ
ልጁ እሱም ወደ ልጅነት ትዝታው የኋልዮሽ ሮጠ ሁሉ
የሚጣፍጥበት ዘመን በራስ መተማመን ጢቅ ብሎ ሞልቶ የሚኮፈስበት ዘመን ትዝ አለው:
ተዋት አትፍረድባት አፍኝው ቻይው ምጥሽን አትናገሪ
አትበሏት ብሶቷን ታውጣው: ሐዘኗን ትግለፀው። እንዲህ ሁናስ መቼ ሰላም ይኖራታል አብራን ትሃድ፤ ተነሽ መስታዋቴ ከለ። ካርለት በተናገረችው ተፀፀተች: አንተነህ ሲናገር ህሊናዋን ሐዘን እንደቁርጥማት አኘካት። መኪናዋ አራቱን ፈላጊዎች ይዛ ወደ ኦሞ
ተንቀሳቀሰች።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የወንዝ ላይ ጉዞውን ከጀመሩ ስምንት ቀን ሞላቸው። ወገቧ ላይ ቢጫ መስመር የተሰመረባት ሰማያዊ ጀልባ በኦሞ ወንዝ ላይ እየተንሳፈፈች ኩዱማ እና ማርኩል መንደሮች አደረሰቻቸው
ኮንችት አያቷ ባስጠናት መረጃ መሰረት በየመንደሩ
እየተዘዋወረች ስታስተውል አያቷ የነገራትን ፍንጭ ባለማግኘቷ ጎዞአቸውን ቀጠሉ።
ሙርሲ ማህበረሰብ ሲደርሱ ወንዶች ፀጉር
የማይወዱ የራስ ፀጉራቸውን የወንድ ብልታቸውን ብብታቸውን
የሚላጩና ፀጉር ማሳደግ እንደ ነውር የሚቆጠርበት
የወንዱን የራሱንም ሆነ የጉያውን ፀጉር መላጨት ያለባት ሴቷ መሆኗንና
ፀጉር ቢያድግ ግን የምትወቀስ ሴቷ እንደምትሆን አዩ።
የሙርሲ ሴቶች ከሸክላ አፈር የተሰራ ክብ ገል ኸንፈራቸው ላይ ጠፍጣፋ እንጨት ጆሮአቸው ላይ ያንጠለጥላሉ: ቁጥሩ
ከአምስት ሺ የማይበልጠው የሙርሲ ማህበረሰብ የተሻለ የግጦሽ ፈና የእርሻ ቦታ በመፈለግ ከቦታ ቦታ የሚዘዋወር ከበርካታ አጎራባቾቹ ጋር በዚሁ የተሻለ ቦታ ለማግኘት ሲንቀሳቀስ የሚጠቃ ማህበረሰብ በመሆኑ በጥንቱ ዘመን ብዙውን ጊዜ የሙርሲ ሴቶች፡ ከብቶቹ
በግጭቱ ወቅት የሚዘርፍና ከሱዳን የሚመጡ ባርያ ፈንጋዮችም ሴቶቹን ስለሚወስዱባቸው ለዚያ መከላከያ የሙርሲ ሴቶች ከሌሎች ሴቶች የተለዩ እንዲሆኑ ገል ከንፈራቸው ላይ እንዲያስገቡ በማድረግ
የሴቶችን ዝርፊያ ማስቆሙ! ይኸ ጠቃሚ ዘዴ በማህበረሰቡ እንዲ
ለመድም ሰፋ ያለ ገል ከንፈራቸው ላይ የሰኩ ልጃገረዶች አነስ ያለ
ገል ካደረጉት ልጃገረዶች የበለጠ ጥሉሽ እንዲከፈልባቸው መደረጉ!
ያ ድርጊት ሴቶች በከንፈራቸውና ጆሮአቸው ገል እንዲሰኩ የተጀመ
ረው ተቀባይነት አግኝቶ እንዲቀጥል አሁን አሁን እንዲያውም ሰፊ
ገል hንፈር ላይ መሰካት ብዙ ጥሉሽ የሚያስገኝ በመሆኑ የቁንጅና
መለኪያ ተደርጎ በውጩ ማህበረሰብ እንደሚገመትም አወቁ።
👍23🥰1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ በኦሞ ወንዝ ሲጓዙ በኡዱማ መርኩል
ጎዋ ኩረምና ሻንጋሮ ያሉትን የቦዲና የሙርሲ መንደሮች ካዩ በኋላ የደቡብ ሱዳንን አቅጣጫ ይጓዝ የነበረው
አቅጣጫውን ከደቡብ ወደ ምስራቅ ድንገት እጥፍ በማድረግ መጓዝ ጀመረ
በአለምአቀፍ አቅጣጫ ማስተካከየዋ ጂፒ ኤስ'
ከሳተላይቶች ጋር ግንኙነት ፈጥራ ያለችበትን የኬክሮስና ኬንትሮስ
ዲግሪ ካወቀች በኋላ ማፑን ስትመለከት በጣም ከሚጠማዘዘው የኦሞ
ወንዝ ጉዞ በኋላ የካራ የሙሩሌ ዳሰነች ማህበረሰቦችና ዝቅ ብሎ
የሚታየው የቱርካና ሐይቅ ብቻ የሚቀራቸው መሆኑን ተረዳች በዚህ ጊዜ ኮንችት ትልቅ ሃሣብ ላይ ወደቀች የአያቷን ቀዬ ለማግኘት የቀራት እድል በጣም ውስን ነው የዳሰነች ማህበረሰብ ያለው ከቱርካና ሐይቅ ጥግ ሲሆን አያቷ ስለሃይቅ ፈፅሞ አንስቶ ስለማያውቅ የሱ ማህበረሰብ ዳሰነች ሊሆን አይችልም ስለዚህ ጥርጣሬዋ ወደ ሁለት ዝቅ አለ ከካራና ከሙረሌ
ከነዚህ አንዱ ካልሆነ ግን የአያቷን ቀዬ ለማግኘት
የምትወስደው አማራጭ
ጭልምልም ያለና ምናልባት ሌሎች ተጨማሪ አመታትን የሚወስድ ይሆናል ስለዚህ ኮንችት ጭንቀት አንገቷን ሲያስደፋት ሶራ ችግሯ ምን እንደሆነ ገብቶት፡-
አዞይሽ ካሰብሽው ትደርሻለሽ" አላት::
ያ ሃሳብ አንዳች ውስጣዊ ሃይል ፈጠረላት አመሰግናለሁ ብላው ጉዟቸውን ቀጠሉ።
ትንሿ ድንኳናቸው ከኦሞ ወንዝ ራቅ ካለ ጉብታም ቦታ አግራር ዛፍ አቅራቢያ ተተክላለች።
ኮንችት ሁለት እግሯን እጥፍጥፍ አድርጋ ድንቁን
የተፈጥሮ ውበት የማታዋን ጀንበርና ልዩ መስህብ የተጎናፀፈውን የዳመናውን ቀለም እያየች የተፈጥሮን ሙዚቃ የአዕዋፍ ዝማሬ
የንፋሱን ሽውሽውታ... ታዳምጣለች።
ይህች አንደበት ያጣች ሃገር ምንኛ ታሳዝናለች። የሌላ
ውበት በውሸታም ካሜራ ቀርፀው ሌላውን እየኮረኮሩ ለማዬት ሲያራኮቱት ኢትዮጵያ ግን እንዲህ ትንፋሽ ቆራጭ የሆነውን
ውበቷን ቆንጥሮ ለዓለም ህዝብ የሚያሳይላት አጣች
ከጥሩው የተበላሸው የሚበዛበት አለማችን ሳታወቅ ከተበላሽው ጥሩው የሚበዛባት አፍሪካ ግን ጨለማ ዳፍንታም
አህጉር ተባለች
“የሚዲያ ልሳን ያልተፈጠረባት ምስኪን ኢትዮጵያ ስለ ውበቷ ማን የራሱን ጥሎ የእሷን ያስተዋውቅላት ታውቃለህ ሶራ ስለ አፍሪካ ዜና በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች ስናይ አንበሳ ሲያገሳ ፏፏቴው ሲንፏፏ... አዕዋፍ ሲበሩ አውሬው ሲተራመስ ይታይና
ኢትዮጵያን የሚመለከት ዜና ሲመጣ ግን ሁሌ ከረጂ ድርጅቶች ዳቦ ሲታደል ማየት ብቻ የሰሃራ በርሃ አገሮች ግመላቸውና አሸዋቸው ሲታይ ኢትዮጵያ ዛፍ አይበቅልባት ፏፏቴም የላት አውሬና አዕዋፍም አይገኙባት የሚባባለው ብዙ ነው።
ለካ ኢትዮጵያ ምንም አላጣች: ሰው ግን ያላት
አይመስለኝም እንደ “ኢብንባቱታ እየዞረ እሚያስተዋውቃት
የላትም..." አለችው እያሸጋገረች አድማሱን አያዬች: ሶራ የሚላት
ጠፋው: ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ስላላቸው ነገር ማለት እንኳን አይችሉም። ብዙ ኢትዮጵያውያን በሌላው ዓለም ይኖራሉ ፧ ግን ስለ አገራቸው ትንፍሽ አይሉም በቅኝ ግዛት የማቀቁት ህዝቦች
አንገታቸውን ቀና አድርገው መዘመር ሲጀምሩ ኢትዮጵያውያን ግን
የተውሶ ካባ ከጃማይካ ተበድረው ትዮጵያዊነታቸውን ከውስጥ
ጃማይካነታቸውን ከላይ ደርበው ተደበቁ። hገሃዱ እውነት ማስመሰሉን መረጡ።' ሶራ አዕምሮው ተረበሸ።
“ተፈጥሮን አትወድም? ሶራ
እስኪ እየው ይህን ውበት?
የሰው ኪነታዊ ጥበብ ምን ብሎ ሊገልጸው ይችላል?" አለችው።
“ያምራል ኮንችት... ብቻ ምን ይሆናል እያለን ያጣን
መሆናችን ያሳዝናል። ለቤት ማስዋቢያ በየግድግዳችን የምንለጥፈው የባህር ማዶ ስዕሉችን ነው። የባር ማዶው ህዝብን ደግሞ አንች እንዳልሽው? “ለመሆኑ አገራችሁ ዛፍ ያበቅላል ወይ! ይሉናል።
“ህይወት ሳናይ ገና የናታችንን ጡት ሳንጠግብ በባህር ማዶህይወት ለሃጫችንን እያዝረበረብን እንነሆልላለን።
“ከዚያ ማነህ? ሲሉን ጸጥ ምን አለህ ሲሉን ቁልጭልጭ በመጨረሻ እነሱም ንቀው እንደ ምራቃቸው ይተፉናል!... የመጣበትን ያላወቀ የደረሰበትን ማን ይጠይቀዋል?.." ብሎ ፀጥ አለ::
ኮንችትና ሶራ እንዲህ በፀጥታ ድባብ ተውጠው ማራኪዋን ተፈጥሮ እየቃኙ የበኩላቸውን ሃሣብ ሲያንሰላስሉ የሆነ ድምፅ
ንፋሱ ይዞ መጣ: እንደገና ድምፁን ጠበቁት ተመልሶ መጣ የወፍ ዝማሬ የወንዝ ኩሉልታ የእፅዋት ሽዋሽዋቴ
አይደለም።የአራዊት ድምፅ… ከሁሉም የተፈጥሮ ቅላፄዎች የተቀነባበረ የሙዚቃ ቃና ነው: ጥዑም ዜማው ይማርካል!
ይስባል! ከተፈጥሮ ጋር ተዋህዶ ልብ ይሰርቃል። ተያዩ ኮንችትና ሶራ: ድምፁ እንደገና እየተስረቀረቀ መጣ። ተጠቃቅሰው ተነስተው ማራኪውን የሙዚቃ ቃና ወደሰሙበት አቅጣጫ ሄዱ።
“ክላሽንኮቭ” መሳሪያውን ጎኑ ያጋደመ ሰው ወይሳውን'
ይነፋል። አዕዋፍ ነፍሳቱ ፀጥ እረጭ ብለው ያዳምጡታል፤ ሶራና
ኮንችትም ከተደበቁበት ሳይወጡ የዜማው እንቅፋት ሳይሆኑ ያን ጥዑም ዜማ በፀጥታ ማዳመጥ ቀጠሉ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ካርለት ካሎ ጎይቲና አንተህ ይመር ከካሮ ማህበረሰቦች
መንደር አንዷ የሆነችው ቆርጮ ዘግይተው ስለተነሱ ከመሸ በኋላ ደረሱ። ከዚያ ወደ መንደሩ ገብተው ሽማግሌዎች ከፀሐይ ቃጠሎ ከሚጠለሉበትና ከሚወያዩበት ኦሞ ወንዝ ዳር ላይ ካለው ዳስ ሄዱ
ቆርጮ ከፍ ብሎ ሜዳማ ከሆነ ቦታ ላይ ያለች መንደር በመሆኗ ለጥ ያለውን የኦሞን ወንዝ ግርጌው ሌላውን የካሮ መንደር ዱሰን ከቀኝ የሙሩሌን ሚዳ ከግራ ማዶው ደሞ የማሽላ
አዝርዕቱን በስተ ምስራቅ ለጥ ያለውን የማንጎ ፓርክ አረንጓዴን ደን ማየት ስለሚቻል ቆርጮ ቀለል ያለችና የተፈጥሮ ውብት በትርኢት መልክ የሚቀርብባት መንደር ናት።
ከሎና አንተነህ ሽማግሌዎችን መጀመርያ ተጥሎ ጎረምሶችን የሐመሩን ደልቲ ገልዲን አይተው እንደሆን ጠየቋቸው በእርግጥ ከጎረምሶች ጥቂቶቹ እንጂ ብዙዎቹ አያውቁትም የሚያውቁት አላየነውም አ
ሲሉ ሌሎቹ ግን ብዙ የሐመር ወንዶች ከከብቶቻቸው ጋር ሙርሌ ያሉ መሆናቸውን ነገሯቸው።
በእርግጥ ይህ ለአንተነህ እንግዳ አልነበረም ዝናብ ሲቀንስና የግጦሽ ሳር ሲጠፋ የሐመር ከብቶች ፍየሎችና በጎች ወደ ኦሞ ወንዝ ይመጣሉ ኦሞ ወንዝ አካባቢ ሳሩ ጥሩ ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ከብቶች የሚጠጡት በቂ ውሃ ከኦሞ ያገኛሉ ስለዚህ የቆርጮ
መንደር ካሮዎች እንደነገራችው ሐመሮች ከብቶታቸው ጋር በሙርሌ ሜዳና በኦሞ ወንዝ ዳር አሉ::
“ታዲያ ምን ይሻላል? አለች ካርለት ከሎንና ጋልተንቤን
የሚሻለውማ ለአንድ ሶስት አራት ቀን እዚሁ አካባቢ
ማጠያየቅ ነው" አላት አንተነህ ይመር ረጋ ብሎ እያንዳንዱን ቃል
እየረጋገጠ፡
ጎይቲ ጆሮዋን በሁለት እጅዋ ይዛ እግሯን አጣጥፋ መሬት ላይ ቁጭ ብላለች:: ደልቲ ቆርጮ መንደር ነኝ ብሎ እንደነገራት ሁሉ ስትመጣ ባለመኖሩና ያለበትም አለመታወቁ ሆዷን አዋለለው ! ሆድ ባሳት...
“እንግዲህ ለዛሬ እዚሁ እንደር ነገና ተነገ ወዲያ ሙርሌ ወርደን እንፈልገውና ተዚያ ወደ ሌሎች የካሮ መንደሮች ዱስና ለቡክ
እንሄድና እንፈልገዋለን!" አለና ጋልታምቤ አያቸው። ሁሉም ተስማሙ፤ ጎይቲ ግን ተነጫነጨች። እሱን ሳታይ ጎኗን ማሳረፍ
አልፈለገችም: ጀግናው እየተንጓለለ እሷ እንቅልፍ እንዴት ያሸልባት? ግን ከአቅሟ በላይ በድምፅ ብልጫ ተሸነፈችና ሁለት
ድንኳናቸውን ዘርግተው ካርለትና ጎይቲ አንዱ ድንኳን ጋልታምቤና ከሎ ደግሞ ሁለተኛው ድንኳን ሊተኙ ተስማሙ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ በኦሞ ወንዝ ሲጓዙ በኡዱማ መርኩል
ጎዋ ኩረምና ሻንጋሮ ያሉትን የቦዲና የሙርሲ መንደሮች ካዩ በኋላ የደቡብ ሱዳንን አቅጣጫ ይጓዝ የነበረው
አቅጣጫውን ከደቡብ ወደ ምስራቅ ድንገት እጥፍ በማድረግ መጓዝ ጀመረ
በአለምአቀፍ አቅጣጫ ማስተካከየዋ ጂፒ ኤስ'
ከሳተላይቶች ጋር ግንኙነት ፈጥራ ያለችበትን የኬክሮስና ኬንትሮስ
ዲግሪ ካወቀች በኋላ ማፑን ስትመለከት በጣም ከሚጠማዘዘው የኦሞ
ወንዝ ጉዞ በኋላ የካራ የሙሩሌ ዳሰነች ማህበረሰቦችና ዝቅ ብሎ
የሚታየው የቱርካና ሐይቅ ብቻ የሚቀራቸው መሆኑን ተረዳች በዚህ ጊዜ ኮንችት ትልቅ ሃሣብ ላይ ወደቀች የአያቷን ቀዬ ለማግኘት የቀራት እድል በጣም ውስን ነው የዳሰነች ማህበረሰብ ያለው ከቱርካና ሐይቅ ጥግ ሲሆን አያቷ ስለሃይቅ ፈፅሞ አንስቶ ስለማያውቅ የሱ ማህበረሰብ ዳሰነች ሊሆን አይችልም ስለዚህ ጥርጣሬዋ ወደ ሁለት ዝቅ አለ ከካራና ከሙረሌ
ከነዚህ አንዱ ካልሆነ ግን የአያቷን ቀዬ ለማግኘት
የምትወስደው አማራጭ
ጭልምልም ያለና ምናልባት ሌሎች ተጨማሪ አመታትን የሚወስድ ይሆናል ስለዚህ ኮንችት ጭንቀት አንገቷን ሲያስደፋት ሶራ ችግሯ ምን እንደሆነ ገብቶት፡-
አዞይሽ ካሰብሽው ትደርሻለሽ" አላት::
ያ ሃሳብ አንዳች ውስጣዊ ሃይል ፈጠረላት አመሰግናለሁ ብላው ጉዟቸውን ቀጠሉ።
ትንሿ ድንኳናቸው ከኦሞ ወንዝ ራቅ ካለ ጉብታም ቦታ አግራር ዛፍ አቅራቢያ ተተክላለች።
ኮንችት ሁለት እግሯን እጥፍጥፍ አድርጋ ድንቁን
የተፈጥሮ ውበት የማታዋን ጀንበርና ልዩ መስህብ የተጎናፀፈውን የዳመናውን ቀለም እያየች የተፈጥሮን ሙዚቃ የአዕዋፍ ዝማሬ
የንፋሱን ሽውሽውታ... ታዳምጣለች።
ይህች አንደበት ያጣች ሃገር ምንኛ ታሳዝናለች። የሌላ
ውበት በውሸታም ካሜራ ቀርፀው ሌላውን እየኮረኮሩ ለማዬት ሲያራኮቱት ኢትዮጵያ ግን እንዲህ ትንፋሽ ቆራጭ የሆነውን
ውበቷን ቆንጥሮ ለዓለም ህዝብ የሚያሳይላት አጣች
ከጥሩው የተበላሸው የሚበዛበት አለማችን ሳታወቅ ከተበላሽው ጥሩው የሚበዛባት አፍሪካ ግን ጨለማ ዳፍንታም
አህጉር ተባለች
“የሚዲያ ልሳን ያልተፈጠረባት ምስኪን ኢትዮጵያ ስለ ውበቷ ማን የራሱን ጥሎ የእሷን ያስተዋውቅላት ታውቃለህ ሶራ ስለ አፍሪካ ዜና በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች ስናይ አንበሳ ሲያገሳ ፏፏቴው ሲንፏፏ... አዕዋፍ ሲበሩ አውሬው ሲተራመስ ይታይና
ኢትዮጵያን የሚመለከት ዜና ሲመጣ ግን ሁሌ ከረጂ ድርጅቶች ዳቦ ሲታደል ማየት ብቻ የሰሃራ በርሃ አገሮች ግመላቸውና አሸዋቸው ሲታይ ኢትዮጵያ ዛፍ አይበቅልባት ፏፏቴም የላት አውሬና አዕዋፍም አይገኙባት የሚባባለው ብዙ ነው።
ለካ ኢትዮጵያ ምንም አላጣች: ሰው ግን ያላት
አይመስለኝም እንደ “ኢብንባቱታ እየዞረ እሚያስተዋውቃት
የላትም..." አለችው እያሸጋገረች አድማሱን አያዬች: ሶራ የሚላት
ጠፋው: ኢትዮጵያውያን በሄዱበት ስላላቸው ነገር ማለት እንኳን አይችሉም። ብዙ ኢትዮጵያውያን በሌላው ዓለም ይኖራሉ ፧ ግን ስለ አገራቸው ትንፍሽ አይሉም በቅኝ ግዛት የማቀቁት ህዝቦች
አንገታቸውን ቀና አድርገው መዘመር ሲጀምሩ ኢትዮጵያውያን ግን
የተውሶ ካባ ከጃማይካ ተበድረው ትዮጵያዊነታቸውን ከውስጥ
ጃማይካነታቸውን ከላይ ደርበው ተደበቁ። hገሃዱ እውነት ማስመሰሉን መረጡ።' ሶራ አዕምሮው ተረበሸ።
“ተፈጥሮን አትወድም? ሶራ
እስኪ እየው ይህን ውበት?
የሰው ኪነታዊ ጥበብ ምን ብሎ ሊገልጸው ይችላል?" አለችው።
“ያምራል ኮንችት... ብቻ ምን ይሆናል እያለን ያጣን
መሆናችን ያሳዝናል። ለቤት ማስዋቢያ በየግድግዳችን የምንለጥፈው የባህር ማዶ ስዕሉችን ነው። የባር ማዶው ህዝብን ደግሞ አንች እንዳልሽው? “ለመሆኑ አገራችሁ ዛፍ ያበቅላል ወይ! ይሉናል።
“ህይወት ሳናይ ገና የናታችንን ጡት ሳንጠግብ በባህር ማዶህይወት ለሃጫችንን እያዝረበረብን እንነሆልላለን።
“ከዚያ ማነህ? ሲሉን ጸጥ ምን አለህ ሲሉን ቁልጭልጭ በመጨረሻ እነሱም ንቀው እንደ ምራቃቸው ይተፉናል!... የመጣበትን ያላወቀ የደረሰበትን ማን ይጠይቀዋል?.." ብሎ ፀጥ አለ::
ኮንችትና ሶራ እንዲህ በፀጥታ ድባብ ተውጠው ማራኪዋን ተፈጥሮ እየቃኙ የበኩላቸውን ሃሣብ ሲያንሰላስሉ የሆነ ድምፅ
ንፋሱ ይዞ መጣ: እንደገና ድምፁን ጠበቁት ተመልሶ መጣ የወፍ ዝማሬ የወንዝ ኩሉልታ የእፅዋት ሽዋሽዋቴ
አይደለም።የአራዊት ድምፅ… ከሁሉም የተፈጥሮ ቅላፄዎች የተቀነባበረ የሙዚቃ ቃና ነው: ጥዑም ዜማው ይማርካል!
ይስባል! ከተፈጥሮ ጋር ተዋህዶ ልብ ይሰርቃል። ተያዩ ኮንችትና ሶራ: ድምፁ እንደገና እየተስረቀረቀ መጣ። ተጠቃቅሰው ተነስተው ማራኪውን የሙዚቃ ቃና ወደሰሙበት አቅጣጫ ሄዱ።
“ክላሽንኮቭ” መሳሪያውን ጎኑ ያጋደመ ሰው ወይሳውን'
ይነፋል። አዕዋፍ ነፍሳቱ ፀጥ እረጭ ብለው ያዳምጡታል፤ ሶራና
ኮንችትም ከተደበቁበት ሳይወጡ የዜማው እንቅፋት ሳይሆኑ ያን ጥዑም ዜማ በፀጥታ ማዳመጥ ቀጠሉ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ካርለት ካሎ ጎይቲና አንተህ ይመር ከካሮ ማህበረሰቦች
መንደር አንዷ የሆነችው ቆርጮ ዘግይተው ስለተነሱ ከመሸ በኋላ ደረሱ። ከዚያ ወደ መንደሩ ገብተው ሽማግሌዎች ከፀሐይ ቃጠሎ ከሚጠለሉበትና ከሚወያዩበት ኦሞ ወንዝ ዳር ላይ ካለው ዳስ ሄዱ
ቆርጮ ከፍ ብሎ ሜዳማ ከሆነ ቦታ ላይ ያለች መንደር በመሆኗ ለጥ ያለውን የኦሞን ወንዝ ግርጌው ሌላውን የካሮ መንደር ዱሰን ከቀኝ የሙሩሌን ሚዳ ከግራ ማዶው ደሞ የማሽላ
አዝርዕቱን በስተ ምስራቅ ለጥ ያለውን የማንጎ ፓርክ አረንጓዴን ደን ማየት ስለሚቻል ቆርጮ ቀለል ያለችና የተፈጥሮ ውብት በትርኢት መልክ የሚቀርብባት መንደር ናት።
ከሎና አንተነህ ሽማግሌዎችን መጀመርያ ተጥሎ ጎረምሶችን የሐመሩን ደልቲ ገልዲን አይተው እንደሆን ጠየቋቸው በእርግጥ ከጎረምሶች ጥቂቶቹ እንጂ ብዙዎቹ አያውቁትም የሚያውቁት አላየነውም አ
ሲሉ ሌሎቹ ግን ብዙ የሐመር ወንዶች ከከብቶቻቸው ጋር ሙርሌ ያሉ መሆናቸውን ነገሯቸው።
በእርግጥ ይህ ለአንተነህ እንግዳ አልነበረም ዝናብ ሲቀንስና የግጦሽ ሳር ሲጠፋ የሐመር ከብቶች ፍየሎችና በጎች ወደ ኦሞ ወንዝ ይመጣሉ ኦሞ ወንዝ አካባቢ ሳሩ ጥሩ ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ከብቶች የሚጠጡት በቂ ውሃ ከኦሞ ያገኛሉ ስለዚህ የቆርጮ
መንደር ካሮዎች እንደነገራችው ሐመሮች ከብቶታቸው ጋር በሙርሌ ሜዳና በኦሞ ወንዝ ዳር አሉ::
“ታዲያ ምን ይሻላል? አለች ካርለት ከሎንና ጋልተንቤን
የሚሻለውማ ለአንድ ሶስት አራት ቀን እዚሁ አካባቢ
ማጠያየቅ ነው" አላት አንተነህ ይመር ረጋ ብሎ እያንዳንዱን ቃል
እየረጋገጠ፡
ጎይቲ ጆሮዋን በሁለት እጅዋ ይዛ እግሯን አጣጥፋ መሬት ላይ ቁጭ ብላለች:: ደልቲ ቆርጮ መንደር ነኝ ብሎ እንደነገራት ሁሉ ስትመጣ ባለመኖሩና ያለበትም አለመታወቁ ሆዷን አዋለለው ! ሆድ ባሳት...
“እንግዲህ ለዛሬ እዚሁ እንደር ነገና ተነገ ወዲያ ሙርሌ ወርደን እንፈልገውና ተዚያ ወደ ሌሎች የካሮ መንደሮች ዱስና ለቡክ
እንሄድና እንፈልገዋለን!" አለና ጋልታምቤ አያቸው። ሁሉም ተስማሙ፤ ጎይቲ ግን ተነጫነጨች። እሱን ሳታይ ጎኗን ማሳረፍ
አልፈለገችም: ጀግናው እየተንጓለለ እሷ እንቅልፍ እንዴት ያሸልባት? ግን ከአቅሟ በላይ በድምፅ ብልጫ ተሸነፈችና ሁለት
ድንኳናቸውን ዘርግተው ካርለትና ጎይቲ አንዱ ድንኳን ጋልታምቤና ከሎ ደግሞ ሁለተኛው ድንኳን ሊተኙ ተስማሙ።
👍14
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ የሰጎን ላባ የተሰካበትን የራስ ጌጥ(ጶሮ) እንደ አቦ ሸማኔ
አይን አሸጋግሮ እየተንተገተገ የሚመለከተውን አይኑን የተተለተለ ሳንቃ ደረቱን እየተመለከቱ ከንፈሩን አሞጥሙጦ የሚያሽለከልከው ትንፋሹ ከፍ ዝቅ በሚሉት ጣቶቹ እያንኳለለ የሚያጣው ስሜተ ሰላቢ ዜማውን ሳይንቀሳሱ ሲያዳምጡ ወይሳ ተጨዋቾቹ ድንገት ዜማውን ቀጥ አደረገና መሳርያውን አንስቶ ሲያቀባብል ሶራና ኮንቺት
ድንግጥ ብለው ሲመለከቱ ድው አድርጎ ሲተኩስ አመዳቸው ቡን ብሎ ነፌሴ አውጪኝ መሬት ላይ ሲንበለበሉ እንደገና ተኮሰ።
ከዚያ ለጥቂጥ ሰአታት ከመሬቷ ጋር ተላትመው ጠበቁና ቀና ብለው ሲመለከቱ ሰውየው ኦሞ ወንዝ ዳር ሄዶ ተረጋግቶ ወንዝ ዳር ሄዶ ቆሟል ኮንቺት እየተሳበች ወደ ሶራ ተጠግታ
"ለምን ተኮሰ? አለች ሶራን።
"አልገባኝም"
"አይቶን ይሆን?"
አይመስለኝም ቢያየን ወይንም ድምፅ ሰምቶረ ቢሆን ኖሮ በሁኔታው ማወቅ እንችል ነበር።
"እሱስ ልክ ነህ ቢገርመኝ እኮ ነው ተረጋግቶ መቆሙም ለጠየቅሁት ጥያቄ ፍንጭ ሰጪ አይደለም ስትለው ከኦሞ ወንዝ ማዶ ድምፅ ተሰማ ሰባቶ ጎረምሶች ናቸው። ወደ ወንዙ ሲጠጉ
"ፃሊ!” አላቸው በካሮኛ ሰላም ናችሁ ለማለት:
'ፃሊና..." አሉትና አምስቱ ወንዙ ዳር እንደቆሙ ፤ ሁለቱ ዳር ላይ የቆመች ቀጠን ብላ ረዘም ያለች የእንጨት ታንኳ ላይ
ወጡና በረጅም ዘንግ ውሃውን ቁልቁል ሲገፉት ታንኳዋ እንደ ውሃ
እናት ውሃውን ወደ ጎን እየሰነጠቀች መጣች::
ለካ የተኮሰው እነሱን ለመጥራት ነው:: ጥሪ በተኩስ አይገርምም!” ስትል ሶራ በአድናቆት ራሱን ወዘወዘ።
“እነሱ ግን እነማን ናቸው?"
"አላውቅም ኮንችት ብናነጋግራቸው ይሻላል?" ሲላት ወዲያው ከተደበቁበት ወጥተው ወደ ሰውዬው ሲጓዙ ፊቱን ዞሮ
የቆመው ሰው የሰው ዳና ሲሰማ ከመቅፅበት መሳሪያውን ከትከሻው
አውርዶ፡-
“ከጠን ማሲዲ" ብሎ መሣሪያውን አቀባብሉ ደገነባቸው።
“ኖት አሱስቴ" አለች ኮንችት በስፓኒሽ እጅዋን እያወዛወዘች ተረጋጋ ለማለት:
ባለመሣሪያው ትኩር ብሎ ሲያያቸው ቆየና “ነጋያ! አለ
ከተቀመጠበት ተነስቶ መሳሪያውን ወደ ትከሻው እየመለሰ: ሶራ ለሰላምታ አፀፋውን መለሰ። “...ሐመር አፎ ዴሲቲኒ" አለው ባለመሣሪያው ሐመርኛ ትችላለህ ለማለት።
ሶራ ፈገግ ብሎ “ሊካ ሊካ ቂንሲዲ...” (ትንሽ ትንሽ
እችላለሁ) አለው። ባለመሳሪያው ፈገግ አለ: ያኔ ነብርነቱ ተለውጦ
እንደ ድንቡሽዬ ህፃን ፈገግታው የሚማርክ ሆነ
ባለመሳሪያውና ኮንችት ከሁለቱ የታንኳዋ ቀዛፊዎች ጋር ተሻግረው ሲጠብቁ ሶራ ጀልባዋን ይዞ ሄደና በጀርባቸው አዝለው
ጀልባዋን ከአምስቱ ጎረምሶች ሁለቱ እየተሳሳቁ ተሸክመው ጫካው
ውስጥ ገቡና በመስመር ሆነው በትላልቅ የግራር የኮሶ... ዛፍ ውስጥ ለውስጥ ትንሽ እንደተጓዙ ኮንችትና ሶራ ዛፍ ላይ እንደ ጦጣ የሚንጨዋለሉ ልጆች አዩ: ቆይቶ ደግሞ በቋንቋቸው ቶሎ ቶሎ
የሚናገሩ ልጃቸውን በቆዳ ብብታቸው ስር ያዘሉ እናቶችና ሽምገል
ያሉ ወንዶችን አዩ።
ጨቅላ ህፃናት ዛፍ ላይ በቆዳ ተንጠልጥለው አንዳንዶቹ ተኝተው እየተቁለጨለጩ ሲወዛወዙ እያዩ እንደ ሄዱ ከርቀት ላይ
የወፍ ጎጆ የሚመስል የኤሊ ቅርፅ ያለው ጎጆ ቤት ተመለከቱ።
ኮንችትን ሲያዩ ህፃናት ወላጆቻቸው ጉያ እየገቡ ወደ መንደራቸው እየሮጡ አለቀሱ: ለኩዩጉ ህፃናት አስፈሪው አውሬ ቀላ ያለ ልብስ ለባሽ ሰው ነው። ከፍ ያሉት ግን የመጣው ይምጣ ብለው በቋንቋቸው ሰላም ቢሏትም ፍርሃታቸው ግን ያስታውቃል: ለጊዜው
ሰላምታቸውን ልብ ብላ አልተከታተለችም ነበር ድንገት አንድ ሽማግሌ፡-
“አሹቃ” ሲሏት አያቷ የነገራት ሰላምታ ትዝ አላት:
ኮንችት አያቷ የሚጠቀምባትን መቀመጫ የመሰለች ሁሉም
ሽማግሌዎችና ወንዶች ይዘው አየች:: ሶራን ዘወር አለችና ምን የሚባሉት ማህበረሰቦች ናቸው?" አለችው ማፕ ላይ ያየችውን ስም ለማስታወስ እየሞከረች:: ሶራ መጀመሪያ ያዩትን ባለ ዋሽንት ጠየቀው።
ሙጉጅዎች ናቸው። እነሱ ግን ራሳቸውን ኩዩጉ ነው
የሚሉት አለው ነገራት ሶራ ለኮንችት። ማፕ ላይ መጉጅም ሆነ ኩዩጉ የሚል እንዳላየች እርግጠኛ ነች: ለማረጋገጥ ግን ወዲያው
ማፕዋን ዘርግታ አየች፤ ሁሉም እሷ ላይ አፈጠጡባት። ማፑ ላይ
የሉም። ካርታው ላይ አየች የሉም፤ ይበልጥ ደነቃት።
ኦኗኗራቸውም ልዩ ነው ፤ የጫካና የወንዝ ዳር ሰዎች: ከመንደሩ እንደደረሱ ሰዉ በአድናቆት ቆሞ አያቸው: ህፃናት ራቅ ብለው ሽሽተው ያያሉ:: አንዱ 'መጡላችሁ' ሲል ሌሎች ህፃናት ደግሞ
እየተሯሯጡ በመላቀስ ይጯጯሃሉ…..
ኮንችት ከጀርባዋ ያዘለችውን ጓዟን አውርዳ ተለቅ ተለቅ ያሉ የአያቷን ፎቶ አወጣች: የዘጠኝ ሰዓት ፀሐይ አሁንም ማቃጠሏ
እንብዛም አልቀነሰም:
ፎቶውን የያዘውን እጅዋን ወደ ህዝቡ ዘረጋችው። ፈሯት፤በምልክት እንኩ' አለቻቸው: ትክ ብለው እያዩ ዝም አሏት ከዚያ ባለዋሽንቱ ውሰዱ' አላቸው በሐመርኛ።
ሶራ ደስ አለው የራሳቸውን የሆነውን ቋንቋ ሲናገሩ
አንድም ቃል ሊገባው አልቻለም ነበር ሐመርኛ ከቻሉ ግን እሱም
ሊያናግራቸው ይችላል። ኩዩጉዎች ግን ሐመርኛን ብቻ አይደለም የሚችሉት። ሙርሲኛ ኒያንጋቶምኛም ይችላሉ።ስለዚህ ሶራ
በሐመርኛ፦
“ውሰዱና እዩ ችግር የለም” አላቸው። አሁንም ዝም ብለው ኮንችትን ሲመለከቷት ቆዩና አንዱ
ሽማግሌ ሌላውን በጆሮው አናገረው ከዚያ ብድግ ብሎ መጣና ተቀበላት።
ፎቶውን ዘቅዝቆ ስለያዘው ኮንችት አስተካክላ ሰጠችው ሽማግሌው ቀረብ እራቅ አድርጎ አየውና በቋንቋው የሆነ ነገር
ተናግሮ ወደ ሀዝቡ ሲጠጋ ለማየት ህዝቡ እንደ ንብ ዙሪያውን ከበበውና ሁካታ ሆነ: ማንም ሌላውን አያዳምጥም።
ከዚያ ሁሉም እነ ኮንችትን ጥለው እንደ ድንጉላ እምም.. እያሉ ወደ አንድ አቅጣጫ ተሯሯጡ: ኮንችትና ሶራ እርስ በርስ
ተያዩ ህዝቡ የሄደበትን ምክንያት ግን ከመካካላቸው ሊመልስ የቻለ አልነበረም።
አንድ ጎጆ ቤት ሲደርሱ ሁሉም ቆሙ። ከውስጥ የሆኑ ሽማግሌ አንጀታቸው ካጥንታቸው ጋር የተጣበቀ አጎንብሰው ወጡ ህዝቡ አሁንም ክብብ አደረጓቸው።
ከዚያ እንደገና ሁካታ ሆነና ጎረምሶች እየተሯሯጡ ርቀው ሄዱ። ፎቶዎችም በልጥ ታስረው ሽማግሌው ከወጡበት ጎጆ ፊት
ለፊት ተንጠለጠሉና ሴቶች ሰማይ ሰማይ እያዩ እልልታውን አቀለጡት ወንዶች እየዘለሉ ጭፈራ ጀመሩ።
ኮንችትና ሶራ እንደገና ተያዩ። ምን እየተሰራ እንደሆነ ማወቅ ተሳናቸው: ባለ ዋሽንቱን ጠየቁት፤ መልስ አጡ። ከዚያ
አራት አምስት መሳሪያ የያዙ ሽቅብ ተኮሱ።
ኮንችትና ሶራ ደነገጡ፡ “ምን እየሰሩ ነው ሶራ?" አለች
የሶራን ትክሻ እየወዘወዘች
በፍርሃት: ሶራ ትከሻው ከፍ ዝቅ አድርጎ አላውቅም አላት በምልክት። ሰው ከየጫካው ተሰባሰበ !
ጥሩንባው እየተነፋ እልል መባል ጀመረ።
ጫካ የሄዱት ጎረምሶች በሾርቃ የሆነ ነገር ይዘው
እየተሯሯጡ መጡ የደከማቸው አይመስሉም የግንባራቸው ደም
ስር ግን ውሃ እንደሽረሸረው የዋርካ ስር አበጥ አበጥ ብሎ በየአቅጣጫው ተጋድሟል። እንደ ተመለሱ ከህዝቡ መሃል ገቡ
ከሌላ ጎጆ ደግሞ ማር የያዘ ትልቅ ቅልና ውሃ ሌሎች ጎረምሶች አመጡ። ውሃውና ማሩ ተቀላቀለና በእንጨት ተማሰለ።
ከዚያ ጥሩንባው እየተነፋ እልል እየተባለ እየተጨፈረ... ሁሉም የሉካዬን ስም እየጠሩ ሰማይ እያዩ ቆዩና ከሲታ ሽማግሌውን አስቀድመው ሶራ ኮንችትና ባለወይሳው ወደ ቆሙት እያሸበሸቡ
እየዘለሉ ጡሩንባው እየተነፋ መጡ።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ኮንችትና ሶራ የሰጎን ላባ የተሰካበትን የራስ ጌጥ(ጶሮ) እንደ አቦ ሸማኔ
አይን አሸጋግሮ እየተንተገተገ የሚመለከተውን አይኑን የተተለተለ ሳንቃ ደረቱን እየተመለከቱ ከንፈሩን አሞጥሙጦ የሚያሽለከልከው ትንፋሹ ከፍ ዝቅ በሚሉት ጣቶቹ እያንኳለለ የሚያጣው ስሜተ ሰላቢ ዜማውን ሳይንቀሳሱ ሲያዳምጡ ወይሳ ተጨዋቾቹ ድንገት ዜማውን ቀጥ አደረገና መሳርያውን አንስቶ ሲያቀባብል ሶራና ኮንቺት
ድንግጥ ብለው ሲመለከቱ ድው አድርጎ ሲተኩስ አመዳቸው ቡን ብሎ ነፌሴ አውጪኝ መሬት ላይ ሲንበለበሉ እንደገና ተኮሰ።
ከዚያ ለጥቂጥ ሰአታት ከመሬቷ ጋር ተላትመው ጠበቁና ቀና ብለው ሲመለከቱ ሰውየው ኦሞ ወንዝ ዳር ሄዶ ተረጋግቶ ወንዝ ዳር ሄዶ ቆሟል ኮንቺት እየተሳበች ወደ ሶራ ተጠግታ
"ለምን ተኮሰ? አለች ሶራን።
"አልገባኝም"
"አይቶን ይሆን?"
አይመስለኝም ቢያየን ወይንም ድምፅ ሰምቶረ ቢሆን ኖሮ በሁኔታው ማወቅ እንችል ነበር።
"እሱስ ልክ ነህ ቢገርመኝ እኮ ነው ተረጋግቶ መቆሙም ለጠየቅሁት ጥያቄ ፍንጭ ሰጪ አይደለም ስትለው ከኦሞ ወንዝ ማዶ ድምፅ ተሰማ ሰባቶ ጎረምሶች ናቸው። ወደ ወንዙ ሲጠጉ
"ፃሊ!” አላቸው በካሮኛ ሰላም ናችሁ ለማለት:
'ፃሊና..." አሉትና አምስቱ ወንዙ ዳር እንደቆሙ ፤ ሁለቱ ዳር ላይ የቆመች ቀጠን ብላ ረዘም ያለች የእንጨት ታንኳ ላይ
ወጡና በረጅም ዘንግ ውሃውን ቁልቁል ሲገፉት ታንኳዋ እንደ ውሃ
እናት ውሃውን ወደ ጎን እየሰነጠቀች መጣች::
ለካ የተኮሰው እነሱን ለመጥራት ነው:: ጥሪ በተኩስ አይገርምም!” ስትል ሶራ በአድናቆት ራሱን ወዘወዘ።
“እነሱ ግን እነማን ናቸው?"
"አላውቅም ኮንችት ብናነጋግራቸው ይሻላል?" ሲላት ወዲያው ከተደበቁበት ወጥተው ወደ ሰውዬው ሲጓዙ ፊቱን ዞሮ
የቆመው ሰው የሰው ዳና ሲሰማ ከመቅፅበት መሳሪያውን ከትከሻው
አውርዶ፡-
“ከጠን ማሲዲ" ብሎ መሣሪያውን አቀባብሉ ደገነባቸው።
“ኖት አሱስቴ" አለች ኮንችት በስፓኒሽ እጅዋን እያወዛወዘች ተረጋጋ ለማለት:
ባለመሣሪያው ትኩር ብሎ ሲያያቸው ቆየና “ነጋያ! አለ
ከተቀመጠበት ተነስቶ መሳሪያውን ወደ ትከሻው እየመለሰ: ሶራ ለሰላምታ አፀፋውን መለሰ። “...ሐመር አፎ ዴሲቲኒ" አለው ባለመሣሪያው ሐመርኛ ትችላለህ ለማለት።
ሶራ ፈገግ ብሎ “ሊካ ሊካ ቂንሲዲ...” (ትንሽ ትንሽ
እችላለሁ) አለው። ባለመሳሪያው ፈገግ አለ: ያኔ ነብርነቱ ተለውጦ
እንደ ድንቡሽዬ ህፃን ፈገግታው የሚማርክ ሆነ
ባለመሳሪያውና ኮንችት ከሁለቱ የታንኳዋ ቀዛፊዎች ጋር ተሻግረው ሲጠብቁ ሶራ ጀልባዋን ይዞ ሄደና በጀርባቸው አዝለው
ጀልባዋን ከአምስቱ ጎረምሶች ሁለቱ እየተሳሳቁ ተሸክመው ጫካው
ውስጥ ገቡና በመስመር ሆነው በትላልቅ የግራር የኮሶ... ዛፍ ውስጥ ለውስጥ ትንሽ እንደተጓዙ ኮንችትና ሶራ ዛፍ ላይ እንደ ጦጣ የሚንጨዋለሉ ልጆች አዩ: ቆይቶ ደግሞ በቋንቋቸው ቶሎ ቶሎ
የሚናገሩ ልጃቸውን በቆዳ ብብታቸው ስር ያዘሉ እናቶችና ሽምገል
ያሉ ወንዶችን አዩ።
ጨቅላ ህፃናት ዛፍ ላይ በቆዳ ተንጠልጥለው አንዳንዶቹ ተኝተው እየተቁለጨለጩ ሲወዛወዙ እያዩ እንደ ሄዱ ከርቀት ላይ
የወፍ ጎጆ የሚመስል የኤሊ ቅርፅ ያለው ጎጆ ቤት ተመለከቱ።
ኮንችትን ሲያዩ ህፃናት ወላጆቻቸው ጉያ እየገቡ ወደ መንደራቸው እየሮጡ አለቀሱ: ለኩዩጉ ህፃናት አስፈሪው አውሬ ቀላ ያለ ልብስ ለባሽ ሰው ነው። ከፍ ያሉት ግን የመጣው ይምጣ ብለው በቋንቋቸው ሰላም ቢሏትም ፍርሃታቸው ግን ያስታውቃል: ለጊዜው
ሰላምታቸውን ልብ ብላ አልተከታተለችም ነበር ድንገት አንድ ሽማግሌ፡-
“አሹቃ” ሲሏት አያቷ የነገራት ሰላምታ ትዝ አላት:
ኮንችት አያቷ የሚጠቀምባትን መቀመጫ የመሰለች ሁሉም
ሽማግሌዎችና ወንዶች ይዘው አየች:: ሶራን ዘወር አለችና ምን የሚባሉት ማህበረሰቦች ናቸው?" አለችው ማፕ ላይ ያየችውን ስም ለማስታወስ እየሞከረች:: ሶራ መጀመሪያ ያዩትን ባለ ዋሽንት ጠየቀው።
ሙጉጅዎች ናቸው። እነሱ ግን ራሳቸውን ኩዩጉ ነው
የሚሉት አለው ነገራት ሶራ ለኮንችት። ማፕ ላይ መጉጅም ሆነ ኩዩጉ የሚል እንዳላየች እርግጠኛ ነች: ለማረጋገጥ ግን ወዲያው
ማፕዋን ዘርግታ አየች፤ ሁሉም እሷ ላይ አፈጠጡባት። ማፑ ላይ
የሉም። ካርታው ላይ አየች የሉም፤ ይበልጥ ደነቃት።
ኦኗኗራቸውም ልዩ ነው ፤ የጫካና የወንዝ ዳር ሰዎች: ከመንደሩ እንደደረሱ ሰዉ በአድናቆት ቆሞ አያቸው: ህፃናት ራቅ ብለው ሽሽተው ያያሉ:: አንዱ 'መጡላችሁ' ሲል ሌሎች ህፃናት ደግሞ
እየተሯሯጡ በመላቀስ ይጯጯሃሉ…..
ኮንችት ከጀርባዋ ያዘለችውን ጓዟን አውርዳ ተለቅ ተለቅ ያሉ የአያቷን ፎቶ አወጣች: የዘጠኝ ሰዓት ፀሐይ አሁንም ማቃጠሏ
እንብዛም አልቀነሰም:
ፎቶውን የያዘውን እጅዋን ወደ ህዝቡ ዘረጋችው። ፈሯት፤በምልክት እንኩ' አለቻቸው: ትክ ብለው እያዩ ዝም አሏት ከዚያ ባለዋሽንቱ ውሰዱ' አላቸው በሐመርኛ።
ሶራ ደስ አለው የራሳቸውን የሆነውን ቋንቋ ሲናገሩ
አንድም ቃል ሊገባው አልቻለም ነበር ሐመርኛ ከቻሉ ግን እሱም
ሊያናግራቸው ይችላል። ኩዩጉዎች ግን ሐመርኛን ብቻ አይደለም የሚችሉት። ሙርሲኛ ኒያንጋቶምኛም ይችላሉ።ስለዚህ ሶራ
በሐመርኛ፦
“ውሰዱና እዩ ችግር የለም” አላቸው። አሁንም ዝም ብለው ኮንችትን ሲመለከቷት ቆዩና አንዱ
ሽማግሌ ሌላውን በጆሮው አናገረው ከዚያ ብድግ ብሎ መጣና ተቀበላት።
ፎቶውን ዘቅዝቆ ስለያዘው ኮንችት አስተካክላ ሰጠችው ሽማግሌው ቀረብ እራቅ አድርጎ አየውና በቋንቋው የሆነ ነገር
ተናግሮ ወደ ሀዝቡ ሲጠጋ ለማየት ህዝቡ እንደ ንብ ዙሪያውን ከበበውና ሁካታ ሆነ: ማንም ሌላውን አያዳምጥም።
ከዚያ ሁሉም እነ ኮንችትን ጥለው እንደ ድንጉላ እምም.. እያሉ ወደ አንድ አቅጣጫ ተሯሯጡ: ኮንችትና ሶራ እርስ በርስ
ተያዩ ህዝቡ የሄደበትን ምክንያት ግን ከመካካላቸው ሊመልስ የቻለ አልነበረም።
አንድ ጎጆ ቤት ሲደርሱ ሁሉም ቆሙ። ከውስጥ የሆኑ ሽማግሌ አንጀታቸው ካጥንታቸው ጋር የተጣበቀ አጎንብሰው ወጡ ህዝቡ አሁንም ክብብ አደረጓቸው።
ከዚያ እንደገና ሁካታ ሆነና ጎረምሶች እየተሯሯጡ ርቀው ሄዱ። ፎቶዎችም በልጥ ታስረው ሽማግሌው ከወጡበት ጎጆ ፊት
ለፊት ተንጠለጠሉና ሴቶች ሰማይ ሰማይ እያዩ እልልታውን አቀለጡት ወንዶች እየዘለሉ ጭፈራ ጀመሩ።
ኮንችትና ሶራ እንደገና ተያዩ። ምን እየተሰራ እንደሆነ ማወቅ ተሳናቸው: ባለ ዋሽንቱን ጠየቁት፤ መልስ አጡ። ከዚያ
አራት አምስት መሳሪያ የያዙ ሽቅብ ተኮሱ።
ኮንችትና ሶራ ደነገጡ፡ “ምን እየሰሩ ነው ሶራ?" አለች
የሶራን ትክሻ እየወዘወዘች
በፍርሃት: ሶራ ትከሻው ከፍ ዝቅ አድርጎ አላውቅም አላት በምልክት። ሰው ከየጫካው ተሰባሰበ !
ጥሩንባው እየተነፋ እልል መባል ጀመረ።
ጫካ የሄዱት ጎረምሶች በሾርቃ የሆነ ነገር ይዘው
እየተሯሯጡ መጡ የደከማቸው አይመስሉም የግንባራቸው ደም
ስር ግን ውሃ እንደሽረሸረው የዋርካ ስር አበጥ አበጥ ብሎ በየአቅጣጫው ተጋድሟል። እንደ ተመለሱ ከህዝቡ መሃል ገቡ
ከሌላ ጎጆ ደግሞ ማር የያዘ ትልቅ ቅልና ውሃ ሌሎች ጎረምሶች አመጡ። ውሃውና ማሩ ተቀላቀለና በእንጨት ተማሰለ።
ከዚያ ጥሩንባው እየተነፋ እልል እየተባለ እየተጨፈረ... ሁሉም የሉካዬን ስም እየጠሩ ሰማይ እያዩ ቆዩና ከሲታ ሽማግሌውን አስቀድመው ሶራ ኮንችትና ባለወይሳው ወደ ቆሙት እያሸበሸቡ
እየዘለሉ ጡሩንባው እየተነፋ መጡ።
👍18😢2👏1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
የኩችሩ መንደር እንደደመቀች ናት:: ብዛት ያላቸው አሣዎች በወጣቶች በጦር ተወጉ ማጅራታቸውን በዱላ ተመቱ በመንጠቆ ተያዙ፤ ሣር በል የሆኑ አራዊት የሜዳ ፍየልና ውድንቢት ታድነው ተገደሉ ፤ ከጫካ ብዛት ያለው ማር ተቆረጠ፤ ቦቆሎና ማሸላ ኦሞ ወንዝ ተወስዶ ተወቃ.. ይበላል ይጠጣል
ይጨፈራል ይመረቃል።
ሉካዬ ሰማይ ላይ ሆኖ ምስሉ እየታዬ ቢሆንም ሶስት ቀን ሙሉ አልመጣም:
“ሎካዬ ለመምጣት ያስባል! ነጩ እባብ ግን “አልመጣም ብሎ አስቸግሮታል ደንቡን ሳናጓድል ሥርዓቱን ብናሟላ ግን ሁለቱም ይመጣሉ" ስላሉ ሽማግሌዎች፣ ሴት ወንዱ ይኳትናል ሰማይ ላይ ላሉት ለሎካዬና ለነጩ እባብ በደስታ ለመፍጠር።
ኮንችት የሎካዬ የልጅ ልጅ መሆኗን ከሰሙም በኋላ
የመንደሩ ሰው ተስብስቦ ከአያቷ ወንድም ቤት ፊት ለፊት ተቀመጡ" የሉካዬ ፎቶ ጎጆው ላይ እንደተንጠለጠለ ነው። ከሥሩሁሌም ግልገል ፍየል ከካሮ እየመጣ ታርዶ ይቀመጥለታል።
ልጃገረዶች ኮንችትን ወደ ጎጆው ቤት ውስጥ ይዘዋት
ገብተው ውስጥ ሱሪዋንና ጡት ማስያዥዋን ሳይቀር አስወለቋት::ከውጭ ይዘፈናል እልል ይባላል. ልጃገረዶች በአኖና የዱር እጣን አላቁጠው ፀጉሯን ሰውነቷን ቀብተው የፍየል ቆዳ አለበሷት: ከዚያ
ይዛው የመጣችውን ልብሷን በእጅዋ እንድታንጠለጥል ሰጧትና ከቤት ወደተሰበሰበው ህዝብ ይዘዋት ወጡ። እሳት ነዷል.
ይጨፈራል... ሁለት ልጃገረዶች አንገታቸውን ደፍተው እጅና እጅዋን
ይዘው ልብሷን ወደ እሳቱ አስወረወሯትና እልልታቸውን ሲያስነኩት
የተሰበሰበው ህዝብ እንደገና ፈነጠዘ ዘለለ አቅራራ.. ጡሩንባ
እልልታ ተኩስ ድብልቅልቅ አለ:
ኮንችት የተረጋጋች አትመስልም። ቆዳዋ ግን አማረባት ጡቶችዋ ቀልተው ቆሙ ለስላሳው ጭኗ... ሁለመናዋ አጓጊ ሆኗል:
ድንጋጤው ስላልለቀቃት ግን ካንገቷ በላይ ውበቷ ቀንሷል።
ሴቱም ወንዱም እየመጣ እጅዋን እየሳመ ደስታውን
እየገለፀላት ወደ ጭፈራው ሲገባ እንደቆዬ ሰው ሰላምታ እየሰጣት
ኩዩጉነቷን አንድነታቸውን እያረጋገጠላት ከሄደ በኋላ ሶራ እየሳቀ ወደ ኮንችት ተጠግቶ አቀፋት: ሽጉጥ አለች ወደ ደረቱ እንደ
እንቦቀቅላ ህፃን፡ አይቷት እንደማያወቅ ሁሉ በሁለት እጆቹ ጡቶችዋን እንደያዘ ፈገግ ብሎ ቁልቁል አያት: ልትስመው ስትል
የሆነች ሴት መጥታ መነጨቀቻት። የኩዩጉ ሴት ወንድን በአደባባይ
አትስምማ!
“እሺ!” አለች ኮንችት
የሴትዮዋ ግሣፄ ስለገባት።
“ለምን ልብሴን አወለቁ? ለምንስ እንዳቃጥለው አደረጉ?''አለችው እሏና ሶራ ከእቅፎቻቸው ከተላቀቁ በኋላ
“የአያትሽን ባህል ረድኤት ለማካፈል! ተፈጥሮአዊ ፀጋሽን ለመመለስ ጎረምሶች ፍቅራቸውን እንደ ወለላ ማር እንዲያውጡሽ….
ለማድረግም" አላት ሶራ እየሳቀ
ባለወይሳው ኮንችትን ባህላዊ ልብስ ለብሳ ሲያያት ደስ አለው። ስለዚ ፈገግ ብሎ ከሌላው ጊዜ በተለዬ ሁኔታ ቀረባትና
ካርለትን አይተሻታል ወይ? ብለህ ጠይቃት" አለው ሶራን።ሶራ የነገረውን ለኮንችት ሲተረጉምላት ተኩስ ተሰማ ተኩሱ
ተደገመ።
ጎረምሶች እየተሯሯጡ ወደ ኦሞ ወንዝ ሄዱ። ጭፈራው
ግን አልቆመም። ባለወይሳው ከሌላ አካባቢ የመጣች ፀጉረ ረጅም
ልብስ ለባሽ... ሁሉ እሱ የሚያውቃትን ካርለትን ያውቃል ብሎ አምኗል።
“ካርለት! ማነች ካርለት? የአባቷስ ስም? ዜግነቷስ?”
ኮንችት በስም ብቻ አውቃለሁ፤ አላውቅም ማለት ትክክል
እንዳልሆነ ታውቃለች: በያገሩ ስንት ካርለት
ዴቪድ... ሊኖር ፥ይችላል። መጀመሪያ ስም አገር ሥራ የሚኖርበት አድራሻ...
ለማንነት መለያ ይጠቅማል: በተረፈ በደፈናው ይከብዳል።ባለወይሳው ግን “አውቃታለሁ' አለማለቷ አስከፋው:
ምን የማረጋት መሰላት ካርለት ልጃገረድ ናት!
ብታጠፋም አላገባኋት ጥሎሽ መክፈል አልጀመርሁ... እና-
አላዝባት አልቀጣት... ይህን እያወቅች መደበቋ ምን ይሉታል? ብሎ አስቦ አዘነባት በኮንችት:
በኦሞ ወንዝ ዳር ካለው ጫካ የሆኑ ሰዎች ብቅ ሲሉ ህዝቡ ተንጫጫ። ኮንችት ቀና ብላ ታይ የኩዩጉ ጎረምሶች እንግዶችን
እየመሩ ይመጣሉ። ለኩዩጉ መንደር በሩ ኦሞ ወንዝ የበሩ ደወል ተኩስ መሆኑ ኮንችትን እንዳስደነቃት ነው።
እንግዶቹ ሲጠጉ አንዷ ነጭ ናት ሁለት ወንዶችና
አንዲት ሴት አብረዋት አሉ። እነሱ ከነጭዋ አንፃር ጥቁር ናቸው።እንግዶቹ እንደቀረቡ ባለወይሳው ዘወር ብሎ አያቸውና ከመቅፅበት
አይኑን እንደ አውሬ አፍጦ አንገቱን እንደ ሰጎን መዘዘው
ሁለቱ ሴቶች ባለወይሳውን ሲያዩ ፊታቸው በደስታ ፀዳል አበራ ቸኩለው ግን ወደ እሱ አልተጠጉም።
ከዚያ ነጯ እንደቆመች ሌላዋ ሴት ቀረብ አለችና፡-
“አያ ደልቲ!'' አለችው
በሐመርኛ:ጎይ ቲ"
ረጋ ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ ላዩ ላይ ተጠመጠመችበት: እቅፍ አድርጓት ቆየና ለቀቃት:: ነጭዋንም ካርለት" ብሉ አቀፋት፤ እሷም አቀፈችው ...
የኩችሩ መንደር ኗሪ በሁኔታው ተደንቆ ጭፈራውን አቁሞ
ያያል።
ካርለት! አለች ወገቧን ወደኋላ ለጥጣ በአድናቆት አፏን እንደከፈተች ኮንችት።
ኮንችት! ካርለት ኮንችትን ከእግር ጥፍሯ እስከ ፀጉሯ
በአድናቆት እያየቻት ቆየችና
“አገኘሻቸው?" አለቻት
“አዎ ተገናኘን” ብላ ኮንችት ሳቀች ተሳሳቁ ኮንችትና
ካርለት! ህዝቡም አብሯቸው ሳቁ! መንደሯም በሣቅ ሙላት ተጥለቀለቀች
“ኮንችት እንዴት ልታገኛቸው ቻልሽ?''
“..በጀልባ ነበር እኔና ሶራ የምንጓዘው፤ እና ባጋጣሚ እዚህ ደረስን
“ማንም ሳይመራሽ?'
“ባገኘሁት ማፕም ሆነ ካርታ ኩዩጉዎች ለመኖራቸው ፍንጭ የሚሰጥ ምልክት የለም:: አያቴ የስጠኝ የአደራ ምልክቶች ግን እንደ ኮኮብ መርተውኛል ያም ሆኖ ግን ባጋጣሚ ኩዩጉዎችን
የሚፈልገው ሰው ተኩሶ እነሱ ሲመጡ ማየት ባንችልና ተጠራጥረን
አብረን ባንመጣ ልፋቴ መና ሆኖ! ስሜቴ በስለት ቢላዋ ለሁለት ተተርትሮ ወደ መጣሁበት እየቆዘምኩ እመለስ ነበር። አጋጣሚው
ግን ረዳን፤ ተገናኘን:
“እንዴት አገኘሻቸው ታዲያ?
“ደግ ሩህሩህና ተግባቢዎች ናቸው:: ኑሯቸው በኦሞ ደለል ላይ ማሸላ በማብቀል ከጫካ ማር በመቁረጥና አሣ በማጥመድ ነው።
ከብት ፍየል የላቸውም፤ ይህ ደግሞ ከብት በሚያረቡት የአጎራባች
ያስንቃቸዋል:: ቁጥራቸው
ማህበረሰቦች ማነሱ ከብት
ባለማርባታቸው የሚያጠቃቸው ብዙ ነው። ስለዚህ የሚኖሩት
በጠባቂ ሞግዚት ነው"
“በሞግዚት?”
“አዎ ካርለት! ጥንት ሞግዚታቸው ካሮ ማህበረሰብ ነበር። አሁን
ግን የካሮዎች ኃይል እየደከመ የኒያንጋቶሞች
(ቡሜዎች) ኃይል እየበረታ በመምጣቱ ኩዩጉዎች ወደ ኒያንጋቶሞች በመጠጋት ከአጎራባች ማህበረሰቦች የሚደርስባቸውን ጥቃት
ሞግዚታቸው ኒያንጋቶሞች ይከላከሉላቸዋል።
“ታዲያ ለሃያሉ ሞግዚታቸው ማር እህል ከሚሰፍሩት ሌላ ልጃገረዶቻቸውን ካለጥሎሽና ካለ አንዳች ክፍያ ኒያንጋቶሞች
በሚስትነት ይሰጣሉ። ኩዩጉዎች ግን ከኒያንጋቶሞች ካሮዎች.. ጋርዐመጋባት አይችሉም ስለሚናቁ።
“ኩዩጉዎች የሌላቸውን የማይመኙ በዚህ ኑሯቸውም ከአቅም በላይ ለሆኑ ነገሮች የማይሰጉና የማይጨነቁ ናቸው። ከሁሉም በላይ ባህላቸውን አክብረው ራሳቸውን ሆነው መኖርን ይመርጣሉ።
የሚገርምሽ በልጅነቱ ከነሱ የተለየው አያቴ እንኳን እንደ
ዘይትና ውሃ ለረጅም ጊዜ ከኖረበት ስልጣኔና ባል ጋር ሳይዋሃድ ነው ወደ መቃብሩ የወረደወ:
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
የኩችሩ መንደር እንደደመቀች ናት:: ብዛት ያላቸው አሣዎች በወጣቶች በጦር ተወጉ ማጅራታቸውን በዱላ ተመቱ በመንጠቆ ተያዙ፤ ሣር በል የሆኑ አራዊት የሜዳ ፍየልና ውድንቢት ታድነው ተገደሉ ፤ ከጫካ ብዛት ያለው ማር ተቆረጠ፤ ቦቆሎና ማሸላ ኦሞ ወንዝ ተወስዶ ተወቃ.. ይበላል ይጠጣል
ይጨፈራል ይመረቃል።
ሉካዬ ሰማይ ላይ ሆኖ ምስሉ እየታዬ ቢሆንም ሶስት ቀን ሙሉ አልመጣም:
“ሎካዬ ለመምጣት ያስባል! ነጩ እባብ ግን “አልመጣም ብሎ አስቸግሮታል ደንቡን ሳናጓድል ሥርዓቱን ብናሟላ ግን ሁለቱም ይመጣሉ" ስላሉ ሽማግሌዎች፣ ሴት ወንዱ ይኳትናል ሰማይ ላይ ላሉት ለሎካዬና ለነጩ እባብ በደስታ ለመፍጠር።
ኮንችት የሎካዬ የልጅ ልጅ መሆኗን ከሰሙም በኋላ
የመንደሩ ሰው ተስብስቦ ከአያቷ ወንድም ቤት ፊት ለፊት ተቀመጡ" የሉካዬ ፎቶ ጎጆው ላይ እንደተንጠለጠለ ነው። ከሥሩሁሌም ግልገል ፍየል ከካሮ እየመጣ ታርዶ ይቀመጥለታል።
ልጃገረዶች ኮንችትን ወደ ጎጆው ቤት ውስጥ ይዘዋት
ገብተው ውስጥ ሱሪዋንና ጡት ማስያዥዋን ሳይቀር አስወለቋት::ከውጭ ይዘፈናል እልል ይባላል. ልጃገረዶች በአኖና የዱር እጣን አላቁጠው ፀጉሯን ሰውነቷን ቀብተው የፍየል ቆዳ አለበሷት: ከዚያ
ይዛው የመጣችውን ልብሷን በእጅዋ እንድታንጠለጥል ሰጧትና ከቤት ወደተሰበሰበው ህዝብ ይዘዋት ወጡ። እሳት ነዷል.
ይጨፈራል... ሁለት ልጃገረዶች አንገታቸውን ደፍተው እጅና እጅዋን
ይዘው ልብሷን ወደ እሳቱ አስወረወሯትና እልልታቸውን ሲያስነኩት
የተሰበሰበው ህዝብ እንደገና ፈነጠዘ ዘለለ አቅራራ.. ጡሩንባ
እልልታ ተኩስ ድብልቅልቅ አለ:
ኮንችት የተረጋጋች አትመስልም። ቆዳዋ ግን አማረባት ጡቶችዋ ቀልተው ቆሙ ለስላሳው ጭኗ... ሁለመናዋ አጓጊ ሆኗል:
ድንጋጤው ስላልለቀቃት ግን ካንገቷ በላይ ውበቷ ቀንሷል።
ሴቱም ወንዱም እየመጣ እጅዋን እየሳመ ደስታውን
እየገለፀላት ወደ ጭፈራው ሲገባ እንደቆዬ ሰው ሰላምታ እየሰጣት
ኩዩጉነቷን አንድነታቸውን እያረጋገጠላት ከሄደ በኋላ ሶራ እየሳቀ ወደ ኮንችት ተጠግቶ አቀፋት: ሽጉጥ አለች ወደ ደረቱ እንደ
እንቦቀቅላ ህፃን፡ አይቷት እንደማያወቅ ሁሉ በሁለት እጆቹ ጡቶችዋን እንደያዘ ፈገግ ብሎ ቁልቁል አያት: ልትስመው ስትል
የሆነች ሴት መጥታ መነጨቀቻት። የኩዩጉ ሴት ወንድን በአደባባይ
አትስምማ!
“እሺ!” አለች ኮንችት
የሴትዮዋ ግሣፄ ስለገባት።
“ለምን ልብሴን አወለቁ? ለምንስ እንዳቃጥለው አደረጉ?''አለችው እሏና ሶራ ከእቅፎቻቸው ከተላቀቁ በኋላ
“የአያትሽን ባህል ረድኤት ለማካፈል! ተፈጥሮአዊ ፀጋሽን ለመመለስ ጎረምሶች ፍቅራቸውን እንደ ወለላ ማር እንዲያውጡሽ….
ለማድረግም" አላት ሶራ እየሳቀ
ባለወይሳው ኮንችትን ባህላዊ ልብስ ለብሳ ሲያያት ደስ አለው። ስለዚ ፈገግ ብሎ ከሌላው ጊዜ በተለዬ ሁኔታ ቀረባትና
ካርለትን አይተሻታል ወይ? ብለህ ጠይቃት" አለው ሶራን።ሶራ የነገረውን ለኮንችት ሲተረጉምላት ተኩስ ተሰማ ተኩሱ
ተደገመ።
ጎረምሶች እየተሯሯጡ ወደ ኦሞ ወንዝ ሄዱ። ጭፈራው
ግን አልቆመም። ባለወይሳው ከሌላ አካባቢ የመጣች ፀጉረ ረጅም
ልብስ ለባሽ... ሁሉ እሱ የሚያውቃትን ካርለትን ያውቃል ብሎ አምኗል።
“ካርለት! ማነች ካርለት? የአባቷስ ስም? ዜግነቷስ?”
ኮንችት በስም ብቻ አውቃለሁ፤ አላውቅም ማለት ትክክል
እንዳልሆነ ታውቃለች: በያገሩ ስንት ካርለት
ዴቪድ... ሊኖር ፥ይችላል። መጀመሪያ ስም አገር ሥራ የሚኖርበት አድራሻ...
ለማንነት መለያ ይጠቅማል: በተረፈ በደፈናው ይከብዳል።ባለወይሳው ግን “አውቃታለሁ' አለማለቷ አስከፋው:
ምን የማረጋት መሰላት ካርለት ልጃገረድ ናት!
ብታጠፋም አላገባኋት ጥሎሽ መክፈል አልጀመርሁ... እና-
አላዝባት አልቀጣት... ይህን እያወቅች መደበቋ ምን ይሉታል? ብሎ አስቦ አዘነባት በኮንችት:
በኦሞ ወንዝ ዳር ካለው ጫካ የሆኑ ሰዎች ብቅ ሲሉ ህዝቡ ተንጫጫ። ኮንችት ቀና ብላ ታይ የኩዩጉ ጎረምሶች እንግዶችን
እየመሩ ይመጣሉ። ለኩዩጉ መንደር በሩ ኦሞ ወንዝ የበሩ ደወል ተኩስ መሆኑ ኮንችትን እንዳስደነቃት ነው።
እንግዶቹ ሲጠጉ አንዷ ነጭ ናት ሁለት ወንዶችና
አንዲት ሴት አብረዋት አሉ። እነሱ ከነጭዋ አንፃር ጥቁር ናቸው።እንግዶቹ እንደቀረቡ ባለወይሳው ዘወር ብሎ አያቸውና ከመቅፅበት
አይኑን እንደ አውሬ አፍጦ አንገቱን እንደ ሰጎን መዘዘው
ሁለቱ ሴቶች ባለወይሳውን ሲያዩ ፊታቸው በደስታ ፀዳል አበራ ቸኩለው ግን ወደ እሱ አልተጠጉም።
ከዚያ ነጯ እንደቆመች ሌላዋ ሴት ቀረብ አለችና፡-
“አያ ደልቲ!'' አለችው
በሐመርኛ:ጎይ ቲ"
ረጋ ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ ላዩ ላይ ተጠመጠመችበት: እቅፍ አድርጓት ቆየና ለቀቃት:: ነጭዋንም ካርለት" ብሉ አቀፋት፤ እሷም አቀፈችው ...
የኩችሩ መንደር ኗሪ በሁኔታው ተደንቆ ጭፈራውን አቁሞ
ያያል።
ካርለት! አለች ወገቧን ወደኋላ ለጥጣ በአድናቆት አፏን እንደከፈተች ኮንችት።
ኮንችት! ካርለት ኮንችትን ከእግር ጥፍሯ እስከ ፀጉሯ
በአድናቆት እያየቻት ቆየችና
“አገኘሻቸው?" አለቻት
“አዎ ተገናኘን” ብላ ኮንችት ሳቀች ተሳሳቁ ኮንችትና
ካርለት! ህዝቡም አብሯቸው ሳቁ! መንደሯም በሣቅ ሙላት ተጥለቀለቀች
“ኮንችት እንዴት ልታገኛቸው ቻልሽ?''
“..በጀልባ ነበር እኔና ሶራ የምንጓዘው፤ እና ባጋጣሚ እዚህ ደረስን
“ማንም ሳይመራሽ?'
“ባገኘሁት ማፕም ሆነ ካርታ ኩዩጉዎች ለመኖራቸው ፍንጭ የሚሰጥ ምልክት የለም:: አያቴ የስጠኝ የአደራ ምልክቶች ግን እንደ ኮኮብ መርተውኛል ያም ሆኖ ግን ባጋጣሚ ኩዩጉዎችን
የሚፈልገው ሰው ተኩሶ እነሱ ሲመጡ ማየት ባንችልና ተጠራጥረን
አብረን ባንመጣ ልፋቴ መና ሆኖ! ስሜቴ በስለት ቢላዋ ለሁለት ተተርትሮ ወደ መጣሁበት እየቆዘምኩ እመለስ ነበር። አጋጣሚው
ግን ረዳን፤ ተገናኘን:
“እንዴት አገኘሻቸው ታዲያ?
“ደግ ሩህሩህና ተግባቢዎች ናቸው:: ኑሯቸው በኦሞ ደለል ላይ ማሸላ በማብቀል ከጫካ ማር በመቁረጥና አሣ በማጥመድ ነው።
ከብት ፍየል የላቸውም፤ ይህ ደግሞ ከብት በሚያረቡት የአጎራባች
ያስንቃቸዋል:: ቁጥራቸው
ማህበረሰቦች ማነሱ ከብት
ባለማርባታቸው የሚያጠቃቸው ብዙ ነው። ስለዚህ የሚኖሩት
በጠባቂ ሞግዚት ነው"
“በሞግዚት?”
“አዎ ካርለት! ጥንት ሞግዚታቸው ካሮ ማህበረሰብ ነበር። አሁን
ግን የካሮዎች ኃይል እየደከመ የኒያንጋቶሞች
(ቡሜዎች) ኃይል እየበረታ በመምጣቱ ኩዩጉዎች ወደ ኒያንጋቶሞች በመጠጋት ከአጎራባች ማህበረሰቦች የሚደርስባቸውን ጥቃት
ሞግዚታቸው ኒያንጋቶሞች ይከላከሉላቸዋል።
“ታዲያ ለሃያሉ ሞግዚታቸው ማር እህል ከሚሰፍሩት ሌላ ልጃገረዶቻቸውን ካለጥሎሽና ካለ አንዳች ክፍያ ኒያንጋቶሞች
በሚስትነት ይሰጣሉ። ኩዩጉዎች ግን ከኒያንጋቶሞች ካሮዎች.. ጋርዐመጋባት አይችሉም ስለሚናቁ።
“ኩዩጉዎች የሌላቸውን የማይመኙ በዚህ ኑሯቸውም ከአቅም በላይ ለሆኑ ነገሮች የማይሰጉና የማይጨነቁ ናቸው። ከሁሉም በላይ ባህላቸውን አክብረው ራሳቸውን ሆነው መኖርን ይመርጣሉ።
የሚገርምሽ በልጅነቱ ከነሱ የተለየው አያቴ እንኳን እንደ
ዘይትና ውሃ ለረጅም ጊዜ ከኖረበት ስልጣኔና ባል ጋር ሳይዋሃድ ነው ወደ መቃብሩ የወረደወ:
👍26❤1👎1🥰1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“ይህ ክላሲካል ዋሽንት ተጫዋች ማነው?"
ሐመሩ የፍቅር ጓደኛዬ ነው ዋሽንት ግን መጫወት
ይችላል?
“ያውም ልብን በሚሰልብ ቅላፄ ነዋ የአጨዋወት ስልቱ ልብሽን የሚሰውርበት አካልሽን የሚያንሳፍፍበት... አንዳች ኃይል አለው:: ከርቀት የሚቀሰቅስሽ የሚንጥሽ…"
“እንኳን ደስ አለሽ በይኛ!በፍቅር ክንዱ አፍቃሪዎቹን
በተራ ያሰለፈን ጀግና በሙዚቃ አርቱም የምንተኛበትንና
የምንነቃበትን ፕሮግራም ያወጣልናላ ደልቲ ገልዲ…
ምን
የሱ ታሪክ ብዙ ነው ኮንችት: በርቀት ስታይው የፍልፈል
አፈር! እየተጠጋሽ ሄደሽ ውስጡ ስትገቢ ግን እንደ ተራራ እየገዘፈ፤ወደላይ እየተከመረ የሚሄድ የሚስጥር ዓለም ነው።''
“እውነትሽን ነው"
“አዎ ኮንችት"
ኮንችት ደነቃት ገረማት ፍቅራቸውን ልታየው ሞከረች አንዴ ካርለትን
ተመልሳ ደልቲን… አየችው አጠጋጋቻቸው አሰተቃቀፈቻቸው
አሳሳመቻቸው… በሃሳቧ ምራቋን እየዋጠች፡፡
“ምነው ኮንችት? ካርለት ኮንችትበብ ጭልጥ ስል
እየሳቀች ቀስቅሳ ጠየቀቻት።
“እንጃ! ግን." ኮንችት ሃሣቧን ገደበችው ዋጠችው ካርለት እንደገና ሳቀች። ሳቋ ደልቲን ጎሻሸመው። ዞር ብሎ ፈገግ
ሲል የኮንችት አይኖች ጥርሶቹ ላይ ተሰኩ! እንደ በረዶ ጥርሱ ነጭ ነው።
“ታፈቅሪዋለሽ?” ሞኝ ሆነች ኮንችት
"አዎ የፍቅር እንጥሌን ሌሎቹ ተንጠራርተው ሲያጡት ተቀምጦ የነካው እሱ ብቻ ነው ተሳሳቁ ካርለትና ኮንችት::
'እንጥሌን እምም...” ኮንችት እንደገና ምራቋን ዋጠች።
“እሱም ያፈቅርሻል?”
“እኔ እንጃ... ቢሆንም አይላኝም እኔ ለእሱ ገና
ያልተገራሁ ባዝራ ነኝ: ስለዚህ ከኔ ይልቅ እሷን ይወዳታል:"
ካርለት በአገጯ ጎይቲን ለኮንችት አሳየቻት
ኮንችት ጎይቲን እስከ አሁን ለምን እንዳላስተዋለቻት
ገረማት የጠይም ቆንጀ እግሮችዋና ወገቧ የሚያምር ችምችም
ያሉት የወተት አረፋ ጥርሶችዋ የሚያስጎመጁ ሆነባት።
ኮንችት ጎይቲን ስታያት እንደቆየች ስለ ውበት አሰበች።ስለ ሰው ልጆች የራቁት ውበት ልብስ ስላልሸፈነው ተፈጥሮአዊ ገላ አለመች:: ሰው ሁሉ በተፈጥሮው ማራኪ ነው ያምራል ይስባል...
“አሁን ግን እሷ አግብታለች ስለዚህ የደልቲን ፍቅር እንደ
ማንጎ እየጋጥሁ እረካባታለሁ ስል ጀግናው ሌላ ቆንጆ በፍቅሩ ግዳይ
ጥሎ ቆንጀዋ ልቡን ሰብራ ልትገባ ስትፈልጠው ደረስሁ... ሳቀች
ካርለት: ሳቋ ኮንችትን ስለውበት ከምታልምበት የፍልስፍና ዓለም ቀሰቀሳት።
"እሷ ደግሞ ማን ናት?"
“ዳራ ትባላለች ሐመር ናት: ልቅም ያለች ቆንጆ!...”
ካርለትና ኮንችት እንዲህ ሲጨዋወቱ ጎይቲ አንተነህ
የምታየው የምትሰማው የምትነካው የምታልመው... አንድ ሰው ነው:: ከፊት ለፊቷ የተቀመጠውን የፍቅር ጀግናዋን ትኩር ብላ
ስታስተውለው ቆይታ ወደ እሱ ሄደች።
በእጇዋ ጨሌ
አንጠልጥላለች መለሎ
አንገቱ ላይ አጠለቀችለት! ቀና ብሎ አያት እሷም ዝቅ ብላ አየችው።
አልተቀየረም እሷም
አልተቀየረችም ትንፋሻቸው ይጥማል። የጫካ ነፃነታቸው ግን የለም ጭኗቿ አይታቀፏትም ደረቱ ላይ አትተኛም፤እሱም ዳሌዋን አያቅፍም
ጡቶችዋ እንደ እንቧይ ደረቱ ላይ አይነጥሩም...
“ይእ! እንኳን ደና ሆነህልኝ እንጂ..." ብላው እንባዋ
በአይኗ ዙሪያ ተኮለኮለ
“ምን ይሆን ብለሽ ነው አንች..." እሱም መናገሩ
አቃተው: ይህን ሲል ጎይቲ የፍቅር ትዝታው ጠቅ አድርጎ ወጋት ስለዚህ ሃዘን የሰራ አካላቷን በጨካኝ ስለቱ አብጠለጠለው። ያኔ ልቧ፣ ሲኮማተር አይኗ ዙሪያ የተኮለኮለው እንባዋ ኩልል ብሎ ወረደ።
“ይእ ባይሆን አልጣህ- አይንህን ልየው ፍቅርህ ልቤ ውስጥ ሲንፈራገጥ አንተ ሳትኖር እንደ ምጥ ያስጮኸኛል ጤና ይነሳኛል። እንኳንም ግን ፍቅርህ ተሆዴ አይወጣ! እንኳንም
አልገላገለው! እሚወለድ ቢሆን ሲያድግ ብቻዬን ጥሎኝ ይሄድ ነበር.." ትክዝ አለች እይታዋን የከለከለውን እንባዋን ጭምቅ አድርጋ
አፍስሳ።
ስሜቷ ጭምትርትር ያለውን ጎይቲን ሲያይ ደልቲም የሆነ
ነገር እሱም ሆድ እንደጉማሬ ሲገላበጥ በዓይነ ህሊናው ታየው።
“ተይው የኔ እህት! ተይው እርሽው ተንግዲህ ተሱ
ምሰይ: የአባት ደንብ ተሁሉም ይቦልጣል ተፍቅርም!! ስለዚህ
ጉም መቼስ አይዘገን.." ብሎ የባሰ የሐዘን ቦይዋን ከፍቶ ለቀቀባት
የሚያጉረመርም ሳግ ቀጥሎ የህሊና ብራቅ ከዚያ እንባዋ አጨቀያት:
ጎይቲ እንገቷን ደፋች: እሱን ማጣቷ እውነት ነው! እውነትም የሱ የመሆን
እድሏ አክትሟል፤
አክትሟል፤እውነትም
የፍቅር ጥገታቸው
ነጥፋለች...
ጎይቲ እንባዋ ቦዩን ይዞ ፈሰሰ፣ እንባ የጠማት መሬት ደግሞ የፍቅር እንባዋን እያጣጣመች ጭልጥ አድርጋ ጠጣችው::መሬት ሰዎች ሲፋቀሩ የሚተርፋት እርግጫቸው ነው ሲያዝኑ ግን ፀሐይ ያቃጠው ጉሮሮዋን ጨዋማ እንባቸው ጥሟን ያረሰርስላታል ጥሟን ይቆርጥላታል ጣፋጩ የሰው ልጅ እንባ የጎይቲን እንባም መሬቷ አፏን ከፍታ ጠጣችው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
' ...ይእ ተወኝ አንተ ሰው! መች አንተ ለእኔ አነስከኝ።
የአንተ መሆኔን ነጋሪ አልሻም ሰው መቼስ ካሉት በረት ሙሉ ከብቶች የሚቆረቆረውና የሚቆጨው አውሬ የበላበትን ጫካ
ያስቀረበትን ከብት አይደል! እንደማያገኘው ልቦናው ያውቀዋል ቢኖርም ለእሱ እስካላለው ድረስ በሽታ ይገለው ይሆናል: ይህን ግን
አያስብም። ዘወትር ቁጭት ብቻ ወይኔ ብቻ. እሮሮ ብቻ
“አያ ደልቲ የኔ አይደለም:: ከእንግዲህ በሴትነት መላዬ
ጀግናውን እየመራሁ ወስጄ ልቤ ውስጥ አላስተኛውም ሙቀቱን አልጋሪውም... ያች የፍቅር ጨረቃ አሁን የማይወለደውን ጨቅላ
አቅፌ እሽሩሩ….' የምልባት ብርሃን ናት: የፍቅሩን ትዝታ!
የጀግናውን ገድል፤ የማይጎረምስ ፍቅሩን፤ ጠረኑ የማይለውጥ
ፍቅሩን... የማልምባት ናት ጨረቃ!
"በእጅ ያረጉት አንባር ከእንጨት ይቆጤራል' እንዲሉ ለአያ ደልቲ ስንሰፈሰፍ ልብህ ቢከፋው አይደንቀኝም!በድየሃለሁ
"ዘንግቼሃለሁ... ግን ወድጄ አይደለም። ስቆምበት ልብህ እንደ ደረቀ
እንጨት ሲሰባበር ይሰማኛል። ወንድነትህን ብታሳዬኝ ሸንቆጥ
ብታደርገኝ አብያው ልቤ አደብ ገዝቶ ትዝታዬን እያረሰ ገለባብጦ የአንተን የፍትር ቡቃያ ያበቅለው ነበር: አንተ ግን ወኔ ከወንድነቱ
ይልቅ ወደ ሴትነቱ ያደላል፡ እንደ ወንዶች አታገሳም አትፎገራምI አትዋጋም አሯሩጠህ አትጥልም! አትጀነንምI የተከደነውን በሃይል አትከፍትም...
“እና ልቤ ሃይ ባይ አጣ ትዝታዬን የሚሽር ትዝታ
አጣሁ ይእ! አይ ልፋቴ አንተ እቅፍ ውስጥ ሆኜ ከተራራው ማዶ ሰው ፍለጋ ስንጠራራ! 'አሁንም ትወጂዋለሽ... እያልህ ከምትለኝ በወንድነት በልቤ ውስጥ የሚዋኘውን ጀግና አጥምደውና ሃሣቤን
ቆልምመው: ለእኔስ አያ ደልቲ እንዳለኝ ተአባቴ ደንብ ውጭ እሱን ማሰብ 'ጉም መዝገን' አይደል!
“አንተና እኔ ሰውነታችን እንጂ አበቃቀላችን ለየቅል ነው።መስሎህ እንጂ ማንም ትሁን ማን የደረሰ ቡቃያዋን አሽቶ ያቃማትን ሐመር አትረሳም:: ያውም ያያ ደልቲን የፋና ወጊውን የጀግናውን አንበሳ ቀጭኔ... ከገደለው እቅፍ የገባችውን... 'ተይ' ተብላ ፍቅሩን ከልቦናዋ አውጥታ ልትወረውረው ይህ የሚቻላት ሐመር የለችም።
“እኔ የኔ ጌታ በቃልህ ተይ ዘንጊው... አትበለኝ: ቅጣትህ ይሻለኛል! ልመናህ ግን ያብሰኛል.." ጎይቲ አይኖችዋን አድማሱ ላይ
ሰንቅራ ሃሳቧን ሳትጨርሰው ፀጥ አለች።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“ይህ ክላሲካል ዋሽንት ተጫዋች ማነው?"
ሐመሩ የፍቅር ጓደኛዬ ነው ዋሽንት ግን መጫወት
ይችላል?
“ያውም ልብን በሚሰልብ ቅላፄ ነዋ የአጨዋወት ስልቱ ልብሽን የሚሰውርበት አካልሽን የሚያንሳፍፍበት... አንዳች ኃይል አለው:: ከርቀት የሚቀሰቅስሽ የሚንጥሽ…"
“እንኳን ደስ አለሽ በይኛ!በፍቅር ክንዱ አፍቃሪዎቹን
በተራ ያሰለፈን ጀግና በሙዚቃ አርቱም የምንተኛበትንና
የምንነቃበትን ፕሮግራም ያወጣልናላ ደልቲ ገልዲ…
ምን
የሱ ታሪክ ብዙ ነው ኮንችት: በርቀት ስታይው የፍልፈል
አፈር! እየተጠጋሽ ሄደሽ ውስጡ ስትገቢ ግን እንደ ተራራ እየገዘፈ፤ወደላይ እየተከመረ የሚሄድ የሚስጥር ዓለም ነው።''
“እውነትሽን ነው"
“አዎ ኮንችት"
ኮንችት ደነቃት ገረማት ፍቅራቸውን ልታየው ሞከረች አንዴ ካርለትን
ተመልሳ ደልቲን… አየችው አጠጋጋቻቸው አሰተቃቀፈቻቸው
አሳሳመቻቸው… በሃሳቧ ምራቋን እየዋጠች፡፡
“ምነው ኮንችት? ካርለት ኮንችትበብ ጭልጥ ስል
እየሳቀች ቀስቅሳ ጠየቀቻት።
“እንጃ! ግን." ኮንችት ሃሣቧን ገደበችው ዋጠችው ካርለት እንደገና ሳቀች። ሳቋ ደልቲን ጎሻሸመው። ዞር ብሎ ፈገግ
ሲል የኮንችት አይኖች ጥርሶቹ ላይ ተሰኩ! እንደ በረዶ ጥርሱ ነጭ ነው።
“ታፈቅሪዋለሽ?” ሞኝ ሆነች ኮንችት
"አዎ የፍቅር እንጥሌን ሌሎቹ ተንጠራርተው ሲያጡት ተቀምጦ የነካው እሱ ብቻ ነው ተሳሳቁ ካርለትና ኮንችት::
'እንጥሌን እምም...” ኮንችት እንደገና ምራቋን ዋጠች።
“እሱም ያፈቅርሻል?”
“እኔ እንጃ... ቢሆንም አይላኝም እኔ ለእሱ ገና
ያልተገራሁ ባዝራ ነኝ: ስለዚህ ከኔ ይልቅ እሷን ይወዳታል:"
ካርለት በአገጯ ጎይቲን ለኮንችት አሳየቻት
ኮንችት ጎይቲን እስከ አሁን ለምን እንዳላስተዋለቻት
ገረማት የጠይም ቆንጀ እግሮችዋና ወገቧ የሚያምር ችምችም
ያሉት የወተት አረፋ ጥርሶችዋ የሚያስጎመጁ ሆነባት።
ኮንችት ጎይቲን ስታያት እንደቆየች ስለ ውበት አሰበች።ስለ ሰው ልጆች የራቁት ውበት ልብስ ስላልሸፈነው ተፈጥሮአዊ ገላ አለመች:: ሰው ሁሉ በተፈጥሮው ማራኪ ነው ያምራል ይስባል...
“አሁን ግን እሷ አግብታለች ስለዚህ የደልቲን ፍቅር እንደ
ማንጎ እየጋጥሁ እረካባታለሁ ስል ጀግናው ሌላ ቆንጆ በፍቅሩ ግዳይ
ጥሎ ቆንጀዋ ልቡን ሰብራ ልትገባ ስትፈልጠው ደረስሁ... ሳቀች
ካርለት: ሳቋ ኮንችትን ስለውበት ከምታልምበት የፍልስፍና ዓለም ቀሰቀሳት።
"እሷ ደግሞ ማን ናት?"
“ዳራ ትባላለች ሐመር ናት: ልቅም ያለች ቆንጆ!...”
ካርለትና ኮንችት እንዲህ ሲጨዋወቱ ጎይቲ አንተነህ
የምታየው የምትሰማው የምትነካው የምታልመው... አንድ ሰው ነው:: ከፊት ለፊቷ የተቀመጠውን የፍቅር ጀግናዋን ትኩር ብላ
ስታስተውለው ቆይታ ወደ እሱ ሄደች።
በእጇዋ ጨሌ
አንጠልጥላለች መለሎ
አንገቱ ላይ አጠለቀችለት! ቀና ብሎ አያት እሷም ዝቅ ብላ አየችው።
አልተቀየረም እሷም
አልተቀየረችም ትንፋሻቸው ይጥማል። የጫካ ነፃነታቸው ግን የለም ጭኗቿ አይታቀፏትም ደረቱ ላይ አትተኛም፤እሱም ዳሌዋን አያቅፍም
ጡቶችዋ እንደ እንቧይ ደረቱ ላይ አይነጥሩም...
“ይእ! እንኳን ደና ሆነህልኝ እንጂ..." ብላው እንባዋ
በአይኗ ዙሪያ ተኮለኮለ
“ምን ይሆን ብለሽ ነው አንች..." እሱም መናገሩ
አቃተው: ይህን ሲል ጎይቲ የፍቅር ትዝታው ጠቅ አድርጎ ወጋት ስለዚህ ሃዘን የሰራ አካላቷን በጨካኝ ስለቱ አብጠለጠለው። ያኔ ልቧ፣ ሲኮማተር አይኗ ዙሪያ የተኮለኮለው እንባዋ ኩልል ብሎ ወረደ።
“ይእ ባይሆን አልጣህ- አይንህን ልየው ፍቅርህ ልቤ ውስጥ ሲንፈራገጥ አንተ ሳትኖር እንደ ምጥ ያስጮኸኛል ጤና ይነሳኛል። እንኳንም ግን ፍቅርህ ተሆዴ አይወጣ! እንኳንም
አልገላገለው! እሚወለድ ቢሆን ሲያድግ ብቻዬን ጥሎኝ ይሄድ ነበር.." ትክዝ አለች እይታዋን የከለከለውን እንባዋን ጭምቅ አድርጋ
አፍስሳ።
ስሜቷ ጭምትርትር ያለውን ጎይቲን ሲያይ ደልቲም የሆነ
ነገር እሱም ሆድ እንደጉማሬ ሲገላበጥ በዓይነ ህሊናው ታየው።
“ተይው የኔ እህት! ተይው እርሽው ተንግዲህ ተሱ
ምሰይ: የአባት ደንብ ተሁሉም ይቦልጣል ተፍቅርም!! ስለዚህ
ጉም መቼስ አይዘገን.." ብሎ የባሰ የሐዘን ቦይዋን ከፍቶ ለቀቀባት
የሚያጉረመርም ሳግ ቀጥሎ የህሊና ብራቅ ከዚያ እንባዋ አጨቀያት:
ጎይቲ እንገቷን ደፋች: እሱን ማጣቷ እውነት ነው! እውነትም የሱ የመሆን
እድሏ አክትሟል፤
አክትሟል፤እውነትም
የፍቅር ጥገታቸው
ነጥፋለች...
ጎይቲ እንባዋ ቦዩን ይዞ ፈሰሰ፣ እንባ የጠማት መሬት ደግሞ የፍቅር እንባዋን እያጣጣመች ጭልጥ አድርጋ ጠጣችው::መሬት ሰዎች ሲፋቀሩ የሚተርፋት እርግጫቸው ነው ሲያዝኑ ግን ፀሐይ ያቃጠው ጉሮሮዋን ጨዋማ እንባቸው ጥሟን ያረሰርስላታል ጥሟን ይቆርጥላታል ጣፋጩ የሰው ልጅ እንባ የጎይቲን እንባም መሬቷ አፏን ከፍታ ጠጣችው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
' ...ይእ ተወኝ አንተ ሰው! መች አንተ ለእኔ አነስከኝ።
የአንተ መሆኔን ነጋሪ አልሻም ሰው መቼስ ካሉት በረት ሙሉ ከብቶች የሚቆረቆረውና የሚቆጨው አውሬ የበላበትን ጫካ
ያስቀረበትን ከብት አይደል! እንደማያገኘው ልቦናው ያውቀዋል ቢኖርም ለእሱ እስካላለው ድረስ በሽታ ይገለው ይሆናል: ይህን ግን
አያስብም። ዘወትር ቁጭት ብቻ ወይኔ ብቻ. እሮሮ ብቻ
“አያ ደልቲ የኔ አይደለም:: ከእንግዲህ በሴትነት መላዬ
ጀግናውን እየመራሁ ወስጄ ልቤ ውስጥ አላስተኛውም ሙቀቱን አልጋሪውም... ያች የፍቅር ጨረቃ አሁን የማይወለደውን ጨቅላ
አቅፌ እሽሩሩ….' የምልባት ብርሃን ናት: የፍቅሩን ትዝታ!
የጀግናውን ገድል፤ የማይጎረምስ ፍቅሩን፤ ጠረኑ የማይለውጥ
ፍቅሩን... የማልምባት ናት ጨረቃ!
"በእጅ ያረጉት አንባር ከእንጨት ይቆጤራል' እንዲሉ ለአያ ደልቲ ስንሰፈሰፍ ልብህ ቢከፋው አይደንቀኝም!በድየሃለሁ
"ዘንግቼሃለሁ... ግን ወድጄ አይደለም። ስቆምበት ልብህ እንደ ደረቀ
እንጨት ሲሰባበር ይሰማኛል። ወንድነትህን ብታሳዬኝ ሸንቆጥ
ብታደርገኝ አብያው ልቤ አደብ ገዝቶ ትዝታዬን እያረሰ ገለባብጦ የአንተን የፍትር ቡቃያ ያበቅለው ነበር: አንተ ግን ወኔ ከወንድነቱ
ይልቅ ወደ ሴትነቱ ያደላል፡ እንደ ወንዶች አታገሳም አትፎገራምI አትዋጋም አሯሩጠህ አትጥልም! አትጀነንምI የተከደነውን በሃይል አትከፍትም...
“እና ልቤ ሃይ ባይ አጣ ትዝታዬን የሚሽር ትዝታ
አጣሁ ይእ! አይ ልፋቴ አንተ እቅፍ ውስጥ ሆኜ ከተራራው ማዶ ሰው ፍለጋ ስንጠራራ! 'አሁንም ትወጂዋለሽ... እያልህ ከምትለኝ በወንድነት በልቤ ውስጥ የሚዋኘውን ጀግና አጥምደውና ሃሣቤን
ቆልምመው: ለእኔስ አያ ደልቲ እንዳለኝ ተአባቴ ደንብ ውጭ እሱን ማሰብ 'ጉም መዝገን' አይደል!
“አንተና እኔ ሰውነታችን እንጂ አበቃቀላችን ለየቅል ነው።መስሎህ እንጂ ማንም ትሁን ማን የደረሰ ቡቃያዋን አሽቶ ያቃማትን ሐመር አትረሳም:: ያውም ያያ ደልቲን የፋና ወጊውን የጀግናውን አንበሳ ቀጭኔ... ከገደለው እቅፍ የገባችውን... 'ተይ' ተብላ ፍቅሩን ከልቦናዋ አውጥታ ልትወረውረው ይህ የሚቻላት ሐመር የለችም።
“እኔ የኔ ጌታ በቃልህ ተይ ዘንጊው... አትበለኝ: ቅጣትህ ይሻለኛል! ልመናህ ግን ያብሰኛል.." ጎይቲ አይኖችዋን አድማሱ ላይ
ሰንቅራ ሃሳቧን ሳትጨርሰው ፀጥ አለች።
👍28❤1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“አፈርሁኝ በራሴ ከሎ!
“ሃፍረት ልብሳችን ሆኗል፡ በተለይ ከዚች ሃገር ወጣ ብለህ ስትመለስ የት ነን? ማን ይዞ አስቀረን?... ሺ ጥያቄ በህሊናሀ ይደረደራል። መልሱን ግን አታገኘውም! የሚመልስልህም የለም::
“መጽሐፍ ስታነብ ያለፉትን የኪነ ጥበብ ስራዎች ስታይ
በታላላቆቻችንና በኛ መካከል ያለው ግሉህ ልዩነት ያፈጥብሃል
ጠልፎ እሚጥል ! ጉቶ ይመስል እንቅፋት ሆኖ ለመስራት የሚፍጨረጨሩትን የሚያደናቅፍ ምክንያት ይኖራል! ደግሞ አለ!
ነበረም።
“ይህ ግን በእንቅልፍ ለመደበቅ በቂ ምክንያት አይደለም ችግር ሲበዛ መፍትሄውም ከውስጡ ይፈለፈላል። ለመሻሻል ምንጩ ችግር እርካታ ማጣት ነው:
“እኛ ግን ብዙ አጥተን ብዙ ነገር ካላቸው በላይ ቆመን
እናናውዛለን። ብቸኛ ሆነን አጠገባችን ያሉትን እናኮርፋለን እንኮንናለን
ከመሃከላችን ለመውጣትና እኛኑ ለመሳብ
የሚንቀሳቀሰውን ሞራል እየስጠን ከማደፋፈር ይልቅ ተጋግዘን በጠረባ እንዘርረዋለን። የኛ ደስታ የሚታየው በወደቀው ስንስቅ ነው ሌሎቹ ደግሞ በእኛ በወደቅነው ይሳለቁብናል።
“ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን ከመከበር ራሳችንን
አራቅን ያለንን አናውቅም! ሌላው ቀርቶ ባለንም አኮራም፡ ከዚያ ይልቅ በተውሶ አልባሳትና ቅራቅንቦ የማስመሰል ተውኔት በባለቤቶቹና በእኛው ህዝብ ፊት እንሰራለን፡ ሁለቱም ግን ረክተው አያጨበጭቡልንም! ከሁለት ያጣ ጎመን' ነን…”
ሶራ በከሎ ሃሳብ መመሰጡና መስማማቱ በሚተናነቀው እልህ ያስታውቃል።
“ሳይጠባበቁ ለስራ መነሳት አስፈላጊ ነው" ብሎ ሶራ ትንሽ አሰብ አደረገና፡-
“ይህችን ሃገር ግን አቅጣጫዋ ወዴት ይሆን የሚለውን ለመመለስ ይከብዳል፤ ወደ ተፈጥሯዊ ሕይወት ወይንስ ወደ ዘመናዊ ኑሮን ሔ? ይህ ሃሳብ በህዝቡ ሲመለስ ህዝቡ ያሰበው ጋ ለመድረስ
መጣጣር ይጀምራል፡ አሁን ግን ያለው ነገር ዝብርቅርቁ የወጣ ነው እስኪ አስበው ጉዟችን እውነት ወዴት ነው? አለና ሃሳቡን ገቶ ከሎን አየው: ሁለቱም ጆሮ ላይ የሚያላዝን ውሻ ጩኸት
የመሰለ ኦምቧረቀ።
“ግን አንድ እውነት አለ፡ አንድ ወቅት የቀደምናቸው
አገሮች አሁን ጥለውን ተፈትልከዋል። እነሱ ዘንድ ለመድረስ ቀጥሎም ለማለፍ በእልህ የታገዘ ጥረት ያስፈልጋል! ከኋላችን
ተነስተው አሁን ከፊት የሚገኙት ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑን ይገባል::
መላና ዘዴ ሳንቀይስ፤ የምንነሳበትንና የምንደርስበትን... ሳናውቅ ግን በለመድናት ጠባብ ጎዳና እንጓዝ ካልን አንዱ መሄጃችን ላይ ገብቶ
ሲሰነቀር ሌላው እንደተለመደው ቆሞ ይቀራል። ለዚህ ሁሉ ግን
ከየት እንጀምር?'' አለ ሶራ ጥያቄ እያቀረበ መልሱን ራሱ ለመመለስ።
“ከራሳችን ከራሳችን መጀመር አለብን" በስሜት ያቀረበው ሃሳብ እንደ ጦር ጎኑን ወጋው። ባዶ ምኞት ወይንስ በተግባር የሚውል ህልም... ፍቅሯ ልቡን እንደ ክትፎ የበላበት ኮንችትስ?
ከሎና ሶራ አንዱ ሌላውን ይበልጥ ለማወቅ፤ ተረዳድተው የአገራቸው አለኝታ ለመሆን ህሊናቸው ቋምጧል: የውጪ ዓለም
ልምዳቸው በራስ መተማመናቸውን ብትንትኑን ቢያወጣቸውም ማንነታቸውን ግን እንደ መስታዋት ቁልጭ አድርጎ አሳይቷቸዋል።
በዚህ የአድቬንቼር ዘመን በትርኪ ምርኪው የግደለሽነት ሕይወት መኖር እንደ አበቅ አንጓሉ አንጓሉ የሐፍረት ቆሻሻ ላይ
እንደሚጥል ተረድተዋል ከሌላው መማር እንጂ እንደ ተውሳክ ጥገኛ መሆን አይንን ጨፍኖ መለመን... በቁም ከመሞት በሞራል
ከመላሸቅ በቀር የሚያመጣው ህሊናዊ ጥጋብ አለመኖሩን ከሕይወት ገጠመኞቻቸው አንፃር አንስተው ብዙ ጊዜ ተጨዋውተዋል::
በህዳሩ የመኸር ወቅት ጨረቃ እንደ ቡሄ ዳቦ ክብ ሆና ገና የብርሃን ወጋገኗን በኒያንጋቶም ተራሮች ወደ ኩዩጉ መንደር ወደ
ኩችሩ ስትፈነጥቅ ከሎና ሶራ እንደተለመደው ሃሳብ ሲለዋወጡ እንደ ቆዩ በመካከላቸው ዝምታ ሰፈነና በእዝነ ሊናቸው ሰማዩ ላይ ጎላ ብሎ የተፃፈ ነገር ተመለከቱ ያን ፅሑፍ ሁለቱም ቀና ብለው አዩት።
“የህይወት ጀልባ ከማዕበል ጋር እየታገለች በውቅያኖሶች ጉያ
አካሏን ነክራ ትንሳፈፋለች ሞት ችግር መከራ ... ያደፍቋታል፤ ደስታ እርካታ ፍቅር. እንደ እንዝርት እያሾሩ ይፈትሏታል እና ጀልባዋ በሁለቱ እጣ ፈንታ ሚዛኗን ጠብቃı የተኙትን የሚስሩት
እየረጋገጧቸው ትሰሩለች:
“በእርገጥ የጎደለው ይተካል ያጣው ያገኛል! ያፈቀረ ይጠላል! የተለጣለ ያነሳል፤የሄደ ይመጣል... በተቃራኒዎች የተወጠረችው ጀልባ የሚፈራረቁባትን ችላ ትጓዛለች።
“አቅጣጫዋ መነሻ መድረሻዋ አይታወቅም:: ጀልባዋ አልቆላታል ትባል እንጂ ከጉዞዋ ከቶ ተገታ አታውቅም: አንድ ቀን
ግን ሥቃይና ሰቆቃ፤ እብሪትና ግፍ የበዛባት ጀልባ ብልሽት
ይገጥማት ይሆናል ያኔ ተሳፋሪዎችዋን ይዛ ትዘቅጣለች ቁልቁል!
“እሪታ ሰማዩን ያቀልጠዋል የቀስተ ዳመና ቀለሞች በሺ
ተባዝተው ሰማዩን ያስውቡታል ከዋክብት ከነበሩበት በታች ዝቅ
ብለው ብርሃናቸውን ያንተገትጋሉ ገነትና መንግሥተ ሰማያት
ይጣመራሉ።
“ሟቹ ያን ውብ ሰማይ ርቆት ሲሄድ እማይጠገብ
ይሆንበታል! ጀልባዋ ስትዘቅጥ ተስፋ የቆረጠ ያለቅሳል... ሰሚና
ጯሂ እንዲሆ በአንድ ጀልባ ሆነው ዋይ ዋይ' ሲሉ ስቃይ እንደ ቅርጫት ላያቸው ላይ ሲከደንባቸው ይወርዳል።
“በዚያ ሰዓት ቅድስት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ሰማይ ትዘረጋለች አምላኳም ድምጿን ሰምቶ ህዝቧን ስለ ስንፍናው አምርሮ ይገስፀዋል።
“እጆቻችሁ ስለምን ሽባ ሆኑ! ስለምንስ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅን መረጣችሁ... ሆድ ብቻ. ጥቅምን ማነፍነፍ ብቻ... ብሎ አዝኖ ውቅያኖሱን ሜዳ ያደርገዋል ድህነትም በምድር ይወርዳል….ልብ ያለው ልብ ይበል" ይላል ሶራና ከሎ አይናቸውን ጨፍነው ያነበቡት።
በጥቁር የሰማይ ሰሌዳ የተፃፈውን ታምር 'ሁለቱም
እየደጋገሙ አነበቡት:
እንግዳው አጋጣሚ
አስገረማቸው አስፈራቸው ... ያ አጉራሽ የለመደው ህሊናቸው ግን ትርጉሙን በጊዜው ሊያቀርብላቸው አልቻለም።
“የምን ጽሑፍ ነው?... ማንስ ፃፈው?...በየግል የፍች "ቀመሩን ለማግኘት ዳንኪራ ረጋጭ ህሊናቸውን አስጨፈሩት። አንዱ
ለሌላው ያየውን ሚስጥር ግን አላወጣም።
ችግርን ለመናድ ማነስ የሚያመጣውን የአዕምሮ ሰንካላነት ለማስቀረት በራስ የመተማመንን ተፈጥሯዊ ፀጋ ጠብቆ ልጅ የልጅ
ልጆችን ከሃፍረት ለማዳን ሆዳምነትን አስወግዶ በእጅና አዕምሮ መጠቀም... ጀልባዋ ሳትሰጥም ደካማ ጎንን ማስተካከል እንደሚገባ
ዘግይተውም ቢሆን የተረዱ ይመስላል።
በዚያች ሰዓት ከሎና ሶራ ተያዩ! ኤርቦሬና ሐመሩ
ሁለቱ አፍሪካውያን ሊግባቡ
ሞከሩ! ሃይላቸውን ለማስተባበር ተቃቀፉደ
ፍቅራቸው ስህተታቸው ቁጭታቸው... ያስፈነደቃት ጨረቃም አላማቸውን ለማጠንhር ብርሃኗን እያሰፋች ፍጥነቷን በመጨር ጥቁሩን ሰማይ እየገለጠች ወደ እነሱ ገሠገሠች።
ከዚያ ያ ኩሩው ድፍርሱ ሚሊዮን ነፍሳትን በውስጡ
አጭቆ ቁልቁል ይሁን ሽቅብ መፍሰሱ ሳይታወቅ በፀጥታ የሚጓዘው ኦሞ ወንዝ በቁጭት አፍ አውጥቶ ሲናገር! እንደ ውሻ ሲጮህ ተሰማ።
"ኢትዮጵያ ፈላስፎቿን ተመራማሪዎቿን የንብ ተምሳሌት ታታሪ ምሁሮቿን, ማቀፍ እርስ በርሳቸው በጡንቻ ሳይሆን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“አፈርሁኝ በራሴ ከሎ!
“ሃፍረት ልብሳችን ሆኗል፡ በተለይ ከዚች ሃገር ወጣ ብለህ ስትመለስ የት ነን? ማን ይዞ አስቀረን?... ሺ ጥያቄ በህሊናሀ ይደረደራል። መልሱን ግን አታገኘውም! የሚመልስልህም የለም::
“መጽሐፍ ስታነብ ያለፉትን የኪነ ጥበብ ስራዎች ስታይ
በታላላቆቻችንና በኛ መካከል ያለው ግሉህ ልዩነት ያፈጥብሃል
ጠልፎ እሚጥል ! ጉቶ ይመስል እንቅፋት ሆኖ ለመስራት የሚፍጨረጨሩትን የሚያደናቅፍ ምክንያት ይኖራል! ደግሞ አለ!
ነበረም።
“ይህ ግን በእንቅልፍ ለመደበቅ በቂ ምክንያት አይደለም ችግር ሲበዛ መፍትሄውም ከውስጡ ይፈለፈላል። ለመሻሻል ምንጩ ችግር እርካታ ማጣት ነው:
“እኛ ግን ብዙ አጥተን ብዙ ነገር ካላቸው በላይ ቆመን
እናናውዛለን። ብቸኛ ሆነን አጠገባችን ያሉትን እናኮርፋለን እንኮንናለን
ከመሃከላችን ለመውጣትና እኛኑ ለመሳብ
የሚንቀሳቀሰውን ሞራል እየስጠን ከማደፋፈር ይልቅ ተጋግዘን በጠረባ እንዘርረዋለን። የኛ ደስታ የሚታየው በወደቀው ስንስቅ ነው ሌሎቹ ደግሞ በእኛ በወደቅነው ይሳለቁብናል።
“ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን ከመከበር ራሳችንን
አራቅን ያለንን አናውቅም! ሌላው ቀርቶ ባለንም አኮራም፡ ከዚያ ይልቅ በተውሶ አልባሳትና ቅራቅንቦ የማስመሰል ተውኔት በባለቤቶቹና በእኛው ህዝብ ፊት እንሰራለን፡ ሁለቱም ግን ረክተው አያጨበጭቡልንም! ከሁለት ያጣ ጎመን' ነን…”
ሶራ በከሎ ሃሳብ መመሰጡና መስማማቱ በሚተናነቀው እልህ ያስታውቃል።
“ሳይጠባበቁ ለስራ መነሳት አስፈላጊ ነው" ብሎ ሶራ ትንሽ አሰብ አደረገና፡-
“ይህችን ሃገር ግን አቅጣጫዋ ወዴት ይሆን የሚለውን ለመመለስ ይከብዳል፤ ወደ ተፈጥሯዊ ሕይወት ወይንስ ወደ ዘመናዊ ኑሮን ሔ? ይህ ሃሳብ በህዝቡ ሲመለስ ህዝቡ ያሰበው ጋ ለመድረስ
መጣጣር ይጀምራል፡ አሁን ግን ያለው ነገር ዝብርቅርቁ የወጣ ነው እስኪ አስበው ጉዟችን እውነት ወዴት ነው? አለና ሃሳቡን ገቶ ከሎን አየው: ሁለቱም ጆሮ ላይ የሚያላዝን ውሻ ጩኸት
የመሰለ ኦምቧረቀ።
“ግን አንድ እውነት አለ፡ አንድ ወቅት የቀደምናቸው
አገሮች አሁን ጥለውን ተፈትልከዋል። እነሱ ዘንድ ለመድረስ ቀጥሎም ለማለፍ በእልህ የታገዘ ጥረት ያስፈልጋል! ከኋላችን
ተነስተው አሁን ከፊት የሚገኙት ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑን ይገባል::
መላና ዘዴ ሳንቀይስ፤ የምንነሳበትንና የምንደርስበትን... ሳናውቅ ግን በለመድናት ጠባብ ጎዳና እንጓዝ ካልን አንዱ መሄጃችን ላይ ገብቶ
ሲሰነቀር ሌላው እንደተለመደው ቆሞ ይቀራል። ለዚህ ሁሉ ግን
ከየት እንጀምር?'' አለ ሶራ ጥያቄ እያቀረበ መልሱን ራሱ ለመመለስ።
“ከራሳችን ከራሳችን መጀመር አለብን" በስሜት ያቀረበው ሃሳብ እንደ ጦር ጎኑን ወጋው። ባዶ ምኞት ወይንስ በተግባር የሚውል ህልም... ፍቅሯ ልቡን እንደ ክትፎ የበላበት ኮንችትስ?
ከሎና ሶራ አንዱ ሌላውን ይበልጥ ለማወቅ፤ ተረዳድተው የአገራቸው አለኝታ ለመሆን ህሊናቸው ቋምጧል: የውጪ ዓለም
ልምዳቸው በራስ መተማመናቸውን ብትንትኑን ቢያወጣቸውም ማንነታቸውን ግን እንደ መስታዋት ቁልጭ አድርጎ አሳይቷቸዋል።
በዚህ የአድቬንቼር ዘመን በትርኪ ምርኪው የግደለሽነት ሕይወት መኖር እንደ አበቅ አንጓሉ አንጓሉ የሐፍረት ቆሻሻ ላይ
እንደሚጥል ተረድተዋል ከሌላው መማር እንጂ እንደ ተውሳክ ጥገኛ መሆን አይንን ጨፍኖ መለመን... በቁም ከመሞት በሞራል
ከመላሸቅ በቀር የሚያመጣው ህሊናዊ ጥጋብ አለመኖሩን ከሕይወት ገጠመኞቻቸው አንፃር አንስተው ብዙ ጊዜ ተጨዋውተዋል::
በህዳሩ የመኸር ወቅት ጨረቃ እንደ ቡሄ ዳቦ ክብ ሆና ገና የብርሃን ወጋገኗን በኒያንጋቶም ተራሮች ወደ ኩዩጉ መንደር ወደ
ኩችሩ ስትፈነጥቅ ከሎና ሶራ እንደተለመደው ሃሳብ ሲለዋወጡ እንደ ቆዩ በመካከላቸው ዝምታ ሰፈነና በእዝነ ሊናቸው ሰማዩ ላይ ጎላ ብሎ የተፃፈ ነገር ተመለከቱ ያን ፅሑፍ ሁለቱም ቀና ብለው አዩት።
“የህይወት ጀልባ ከማዕበል ጋር እየታገለች በውቅያኖሶች ጉያ
አካሏን ነክራ ትንሳፈፋለች ሞት ችግር መከራ ... ያደፍቋታል፤ ደስታ እርካታ ፍቅር. እንደ እንዝርት እያሾሩ ይፈትሏታል እና ጀልባዋ በሁለቱ እጣ ፈንታ ሚዛኗን ጠብቃı የተኙትን የሚስሩት
እየረጋገጧቸው ትሰሩለች:
“በእርገጥ የጎደለው ይተካል ያጣው ያገኛል! ያፈቀረ ይጠላል! የተለጣለ ያነሳል፤የሄደ ይመጣል... በተቃራኒዎች የተወጠረችው ጀልባ የሚፈራረቁባትን ችላ ትጓዛለች።
“አቅጣጫዋ መነሻ መድረሻዋ አይታወቅም:: ጀልባዋ አልቆላታል ትባል እንጂ ከጉዞዋ ከቶ ተገታ አታውቅም: አንድ ቀን
ግን ሥቃይና ሰቆቃ፤ እብሪትና ግፍ የበዛባት ጀልባ ብልሽት
ይገጥማት ይሆናል ያኔ ተሳፋሪዎችዋን ይዛ ትዘቅጣለች ቁልቁል!
“እሪታ ሰማዩን ያቀልጠዋል የቀስተ ዳመና ቀለሞች በሺ
ተባዝተው ሰማዩን ያስውቡታል ከዋክብት ከነበሩበት በታች ዝቅ
ብለው ብርሃናቸውን ያንተገትጋሉ ገነትና መንግሥተ ሰማያት
ይጣመራሉ።
“ሟቹ ያን ውብ ሰማይ ርቆት ሲሄድ እማይጠገብ
ይሆንበታል! ጀልባዋ ስትዘቅጥ ተስፋ የቆረጠ ያለቅሳል... ሰሚና
ጯሂ እንዲሆ በአንድ ጀልባ ሆነው ዋይ ዋይ' ሲሉ ስቃይ እንደ ቅርጫት ላያቸው ላይ ሲከደንባቸው ይወርዳል።
“በዚያ ሰዓት ቅድስት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ሰማይ ትዘረጋለች አምላኳም ድምጿን ሰምቶ ህዝቧን ስለ ስንፍናው አምርሮ ይገስፀዋል።
“እጆቻችሁ ስለምን ሽባ ሆኑ! ስለምንስ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅን መረጣችሁ... ሆድ ብቻ. ጥቅምን ማነፍነፍ ብቻ... ብሎ አዝኖ ውቅያኖሱን ሜዳ ያደርገዋል ድህነትም በምድር ይወርዳል….ልብ ያለው ልብ ይበል" ይላል ሶራና ከሎ አይናቸውን ጨፍነው ያነበቡት።
በጥቁር የሰማይ ሰሌዳ የተፃፈውን ታምር 'ሁለቱም
እየደጋገሙ አነበቡት:
እንግዳው አጋጣሚ
አስገረማቸው አስፈራቸው ... ያ አጉራሽ የለመደው ህሊናቸው ግን ትርጉሙን በጊዜው ሊያቀርብላቸው አልቻለም።
“የምን ጽሑፍ ነው?... ማንስ ፃፈው?...በየግል የፍች "ቀመሩን ለማግኘት ዳንኪራ ረጋጭ ህሊናቸውን አስጨፈሩት። አንዱ
ለሌላው ያየውን ሚስጥር ግን አላወጣም።
ችግርን ለመናድ ማነስ የሚያመጣውን የአዕምሮ ሰንካላነት ለማስቀረት በራስ የመተማመንን ተፈጥሯዊ ፀጋ ጠብቆ ልጅ የልጅ
ልጆችን ከሃፍረት ለማዳን ሆዳምነትን አስወግዶ በእጅና አዕምሮ መጠቀም... ጀልባዋ ሳትሰጥም ደካማ ጎንን ማስተካከል እንደሚገባ
ዘግይተውም ቢሆን የተረዱ ይመስላል።
በዚያች ሰዓት ከሎና ሶራ ተያዩ! ኤርቦሬና ሐመሩ
ሁለቱ አፍሪካውያን ሊግባቡ
ሞከሩ! ሃይላቸውን ለማስተባበር ተቃቀፉደ
ፍቅራቸው ስህተታቸው ቁጭታቸው... ያስፈነደቃት ጨረቃም አላማቸውን ለማጠንhር ብርሃኗን እያሰፋች ፍጥነቷን በመጨር ጥቁሩን ሰማይ እየገለጠች ወደ እነሱ ገሠገሠች።
ከዚያ ያ ኩሩው ድፍርሱ ሚሊዮን ነፍሳትን በውስጡ
አጭቆ ቁልቁል ይሁን ሽቅብ መፍሰሱ ሳይታወቅ በፀጥታ የሚጓዘው ኦሞ ወንዝ በቁጭት አፍ አውጥቶ ሲናገር! እንደ ውሻ ሲጮህ ተሰማ።
"ኢትዮጵያ ፈላስፎቿን ተመራማሪዎቿን የንብ ተምሳሌት ታታሪ ምሁሮቿን, ማቀፍ እርስ በርሳቸው በጡንቻ ሳይሆን
👍18👏1🤔1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ካርለት ከዳንሱ ቦታ ራቅ ብላ ጀግናዋን በአይኖቿ
ስትፈልገው በጆሮዋ ስልምልም የሚያደርግ የሙዚቃ ቃና ሰማች።
እንግዳ ነው ያ ሙዚቃ ለጆሮዋ! ሳባት ሙዚቃው
ተጎተተችለት: ቃናው ጆሮዋን እየላሳት ወደ ውስጧ ዘለቀ የህሊናዋን ጓዳ! የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው። አሻት፤ ዳሰሳት…..እሷም
አንኳኳ የሆሊናዋን ጓዳ የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው አሻት፤ ዳሰሳት
ሁለመናዋን ነካካው
አንሸራተታት ደመቅ
ደመቅመቅ... የሚለው ዜማ ፍል ውኃ ውስጥ እንደገባች ሁሉ ቁልቁል እየፈሰሰ ሰውነቷን አጋላት ደስ አላት ሰውነቷ ሲግል‥. ጡቶችዋ ግን ተቆጥተው ቆሙ፤ ዳሌዋ አኩሩፎ አበጠ ፤ ጭኗ አዝኖ ለሰለሰ… ሙዚቃና ልብ ወለድ ጽሑፍ ካለ እሳት ሰውነቷን ሲያጋግሉት ደስ ይላታል... የረሳችው ስሜት
ፈረሰኛው አረፋ እንደሚያስደፍቀው ወራጅ ወንዝ ሞተሯን አሽከረከረው፤ አቃሰተች ያኔም ስርቅርቁ ዜማ በጆሮዋ መግባቱን
አላቆመም:
እየቀረበች ስትሄድ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ወይሳውን እየነፋ ጥዑም ዜማ የሚያወጣውን ጀግና አየችው። የሙዚቃው
ቅላፄ እንደ “ቤቶሆቨን ሞዛርት ሲንፎኒ" ቃናው እየቆዬ ጣማት።እሰይ እሱ ነው ብላ አጉተመተመች..
ከዚያ ዱካዋን አጥፍታ በሙዚቃው ስልት እርምጃዋን አስተካክላ ተጠጋችው፡
ባለወይሳው አይኖቹ ከጨረቃና ከዋክብቱ ጋር ይጫወታሉ ቅላፄው
ወዲያና ወዲህ ይመላለሳል። ሙዚቃው እንኳን ሌላውን ራሱንም
መስጦታል። እውነተኛ የኪነ ጥበብ ሥራ ውጤት ስቃይና ደስታዋ፤ሐዘንና ትካዜዋ. እፍታውን ቀማሹ ጣዕሙን አስተካካዩና ፈጣሪው
ያኔው ነውና ወይሳው ደልቲን መስጦታል! ወጥሮታል...
ካርለት ደልቲን በሚጫወተው የሙዚቃ ቃና ተመስጦ በማየቷ ይበልጥ ወደደችው፡ ደልቲ
ለስሜቱ ታማኝ ነው አይቀጥፍም አያስመስልም...
ስርቅርቁ የሙዚቃ ቃና
የሚንቆረቆረው ለህሊናው እርካታ ነው::
ካርለትን የሙዚቃው ስልት አቅም አሳነሳት: ሁለመናዋ
እንቅስቃሴ ፍጥነቱን ስለጨመረ ደካከመች: ስሜቷን አፋጭቶ
ሃይሏን መልሶ ለመሳል አጋዥ ያስፈልጋታል
ባለወይሳው ያን ሰው አጥታው ከርማለች! አሁን ግን አጠገቧ ነው።
እጆችዋ ትከሻው ላይ አረፉ። ባለወይሳው ስርቅርቅ ዜማውን አቁሞ ቀና ብሎ አያት። ቆዳዋ ተገልቧል፣ ከርቀት ጠቆር
ብለ የታየው አካሏ ቁልቁል ወደሱ ሲመጣ እየጎላ ታየው። የራቀው
ሽለቆ ቀረበው።
ንጥት ያለው ገላዋ በተለይም ጭኗን ትክ ብሎ እያዬ፡ “ካርለትት አላትና አይኖቹ ሳቁ። ሃይል ያጣችው ካርለት
የተሸበሸበ ርጥብ ከንፈሯን ለጠጥ አርጋ ደካማ ፈግታዋን አሳየችው።
ባለወይሳው አስተውሎ አያት ውስጧንም አየው
የተቀጣጠለውን ስሜቷን ነካው፡
ጭኖቹ ላይ ያለውን ወይሳ አንስቶ ለጨረቃ ሰጣት!
ጨረቃም ወይሳውን ተቀብላ እየነፋች ጥዑም ዜማዋን ማንቆርቆር ጀመረች። በጨረቃ የሙዚቃ ቃና ደልቲ ቀኝ እጁ እየተንከላወሰ ወደ
ነጩ ጭኗ ገባ። ነዘራት
በሽተኛዋን! “በሽታውን የደበቀ..." እንዲሉ እሷም ሃኪሟን ረዳችው የሚያቃጥላትን የሚቆረጥማትን እጁን
በእጅዋ ይዛ አሳየችው።
ጆሮ ግንዱን ፀጉሩን
ማጅራቱን...እየደባበሰች የእርዳኝ ጥሪዋን አሰማችው። ሀኪሟ በስሜቷ እሱም ተሽፈነ። ለጋራ በሽታቸው ግን የሚበጀውን ያውቃል። ስለዚህ ማገገሚያ ቀንዱን አቁሞ ይዞ ከተቀመጠበት ተነሳ።
ሙዚቃው ይስረቀረቃል! ዳንሱ ጦፏል... ጨረቃ
ታዜማለች ! ቅጠሉ እስክስታ ይወርዳል! ነፋሱ አታሞውን
ይደልቃል... ጥቁርና ነጭ ቀለሙ ማራኪ ዜብራም ያናፋል...
ኮንችት ጭፈራውን በጉጉት እያየች እንደቆየች ስለ ነገው
ጉዟቸው ካርለትን ለመጠየቅ ፈልጋ አጣቻት የኩችሩ መንደር ኗሪ
ጥበቃውን አላቆመም። ነጩ እባብና ሎካዬ ግን አልመጡም። ኮንችት
በየዋህነታቸው ብታዝንም ማድረግ የምትችለው ባለመኖሩ በዝምታ
ሁኔታውን ስትከታተል ሰነበተች። የመቆያ ፈቃዷ እያለቀ ነው:: ስፔን ስትመለስ ብዙ ልትሰራ አስባለች በተለይ ስለ ኢትዮጵያ ስለ ኩጉዩ፡ ከመሄዷ በፊት ግን ሐመርን ኤርቦሬን ከካርለት ጋር በሷ
መኪና ለማየት ተስማምታለች ጉዞዋን በተመለከተ ግን ከካርለት
ጋር መነጋገር ያለባት ቁም ነገር ነበር።
ኮንቺት ካርለትን ስታጣት ደልቲን በጨረቀዋ ብርሃን ፈለገችው የለም:
ካርለት የሄደችው እሱ ዘንድ ይሆን?' አብረው ሆነው
ለማየት ጓጓች: ፍቅር ሲለዋወጡ እንዴት ይሆን?' ለማስብ ሞከረች:: መልሳ ደግሞ ሃጢያት እንደሰራች ሁሉ አስበችው አፈረች። ሆኖም ግን አልቻለችም ጉጉቷ ጨመረ።
በዚህ መካከል ድክምክም ያለውን የወይሳውን ድምፅ
ኮንችት ከርቀት ሰማችው። በድፍረት ሄደች ወደ ጫካው! ድንገት ግን ክው ኦለች ! ባለበት የሚሰግር
ዜብራ አየች ፈራችው
ዜብራውን ይጋልባል ... በስሜት ተውጣ አይኖችዋን ጨፈነች:
"...የፍቅር እንጥሌን ሌሎች ተንጠራርተው ሲያጡት የነካው እሱ ብቻ ነው" ኮንችትን የነገረቻት ትዝ አላት።
“ዋው! ጎመጀች በዜብራው
ግልቢያውን አሰጋገሩን
አደነቀችው። ወደደችው ያን ስሜት ሰላቢ ጥዑም ዜማ... ፈውስ ሰጭ ዳንኪራ… ንፁህ የጫካ ፍቅር... ማራኪ ተፈጥሮ ተጋግዘው እንግዳዋን መልሀቋን አስጥለው በጉጉት ገተሯት! ተጣራች በሲቃ ሶራ ግን አልሰማትም! ኤጭ! ብላ ከንፈሯን ጣለች። ጎደሎነት
ተሰማት ያማራትን የዜብራ ግልቢያ ግን የሚያቀምሳት አጣች.የጎመጀችለትን ያጣችው ኮንችት አዘነች። ...ዛፉ ቅጠሉም አዘነላት ላልተጠራችው ተመልካች!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“እ. እ..." አቃሰቱ እምቡዋ እ. እ" ሳግ ተናነቃቸው
ህፃናት ወጣቶች አዛውንቶች ኦሞ ወንዝ ዳር ጫካ ተሰባስበው እንግዶች በእንጨቷ ታንኳ ኦሞን ሲያቋርጡ አያቸው።
ኮንችት እጅዋን አውለበለበችላቸው “ቻው... ባባይ... አለቻቸው። ዝም አሉ ኩዩጉዎች የነሱ የጥልቅ ፍቅር መግለጫቸው ዝምታ ነው። ሳግ ያበት “እ... እ..." እሚያሰኝ ከጥጃዋ በሃይል እንደተነጠለች ላም የሚያንሰፈስፍ ዝምታ! “እ. እ. እምቡዋ.. እያሰኘ የማይፈስ እንባ የሚያስነባ, የማይገልፁት ግን የሚታይ
የሚነካ... የመለየት ጭንቀት የሚታይበት ስሜት..
“እወዳችኋለሁ! ከናንተ በመለየቴ አዝናለሁ. ምንጊዜም አልረሳችሁም..." ኮንችት በስፓኒሽ ለመግለፅ ለፈለፈች¦ ምላሽ ግን
አልነበረም። “ፀጥታ ብቻ! ለኩዩጉዎች የመለየትን መጥፎነት የሚገልፅ ቋንቋ የላቸውም ካለ ዝምታ በቀር።
ኮንችት አነባች::
የካርለትን ትከሻ ተደግፋ አነባች አለቀለች ሌሎች ግን ዝም ረጭ ብለዋል እንደ ሌሎች ወንዞች
የማይጮኸው የማይደነፋው.
የኩዩጉዎች ህይወት የመልክ ማያ መስታዋታቸው የሆነው የኦሞ ወንዝም በዝምታ ድባብ እንደ ተዋጠ
ነው: ወፎች ግን ይበራሉ ያዜማሉ! እዕዋት ያሽበሽባሉ...
“እሷ ሄደች በሉ
ሉካዬንና የሰላም አድባራችን
የነበረውን ነጩን እባብ እንጠብቅ ! ተከፍተን ታዩን መምጣቱን እንዳይተዉት እንዝፈን እንጫወት.."
ሽማግሌዎች ለኩችሩ መንደር ህዝባችው ተናገሩ ኮንችት ካርለት ከሎ ሶራ… ኦሞን ከተሻገሩ በኋላ ዞር ብለው አዩ: ኩዩጉዎች የሉም!.ሲደልቁ ግን ይሰማል ለዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ለረጅም ጊዜ አልቅሶና አዝኖስ መኖር እንዴት ይቻላል!
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ካርለት ከዳንሱ ቦታ ራቅ ብላ ጀግናዋን በአይኖቿ
ስትፈልገው በጆሮዋ ስልምልም የሚያደርግ የሙዚቃ ቃና ሰማች።
እንግዳ ነው ያ ሙዚቃ ለጆሮዋ! ሳባት ሙዚቃው
ተጎተተችለት: ቃናው ጆሮዋን እየላሳት ወደ ውስጧ ዘለቀ የህሊናዋን ጓዳ! የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው። አሻት፤ ዳሰሳት…..እሷም
አንኳኳ የሆሊናዋን ጓዳ የስርቆሽ በሯን ከፍታ አስገባችው አሻት፤ ዳሰሳት
ሁለመናዋን ነካካው
አንሸራተታት ደመቅ
ደመቅመቅ... የሚለው ዜማ ፍል ውኃ ውስጥ እንደገባች ሁሉ ቁልቁል እየፈሰሰ ሰውነቷን አጋላት ደስ አላት ሰውነቷ ሲግል‥. ጡቶችዋ ግን ተቆጥተው ቆሙ፤ ዳሌዋ አኩሩፎ አበጠ ፤ ጭኗ አዝኖ ለሰለሰ… ሙዚቃና ልብ ወለድ ጽሑፍ ካለ እሳት ሰውነቷን ሲያጋግሉት ደስ ይላታል... የረሳችው ስሜት
ፈረሰኛው አረፋ እንደሚያስደፍቀው ወራጅ ወንዝ ሞተሯን አሽከረከረው፤ አቃሰተች ያኔም ስርቅርቁ ዜማ በጆሮዋ መግባቱን
አላቆመም:
እየቀረበች ስትሄድ በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ወይሳውን እየነፋ ጥዑም ዜማ የሚያወጣውን ጀግና አየችው። የሙዚቃው
ቅላፄ እንደ “ቤቶሆቨን ሞዛርት ሲንፎኒ" ቃናው እየቆዬ ጣማት።እሰይ እሱ ነው ብላ አጉተመተመች..
ከዚያ ዱካዋን አጥፍታ በሙዚቃው ስልት እርምጃዋን አስተካክላ ተጠጋችው፡
ባለወይሳው አይኖቹ ከጨረቃና ከዋክብቱ ጋር ይጫወታሉ ቅላፄው
ወዲያና ወዲህ ይመላለሳል። ሙዚቃው እንኳን ሌላውን ራሱንም
መስጦታል። እውነተኛ የኪነ ጥበብ ሥራ ውጤት ስቃይና ደስታዋ፤ሐዘንና ትካዜዋ. እፍታውን ቀማሹ ጣዕሙን አስተካካዩና ፈጣሪው
ያኔው ነውና ወይሳው ደልቲን መስጦታል! ወጥሮታል...
ካርለት ደልቲን በሚጫወተው የሙዚቃ ቃና ተመስጦ በማየቷ ይበልጥ ወደደችው፡ ደልቲ
ለስሜቱ ታማኝ ነው አይቀጥፍም አያስመስልም...
ስርቅርቁ የሙዚቃ ቃና
የሚንቆረቆረው ለህሊናው እርካታ ነው::
ካርለትን የሙዚቃው ስልት አቅም አሳነሳት: ሁለመናዋ
እንቅስቃሴ ፍጥነቱን ስለጨመረ ደካከመች: ስሜቷን አፋጭቶ
ሃይሏን መልሶ ለመሳል አጋዥ ያስፈልጋታል
ባለወይሳው ያን ሰው አጥታው ከርማለች! አሁን ግን አጠገቧ ነው።
እጆችዋ ትከሻው ላይ አረፉ። ባለወይሳው ስርቅርቅ ዜማውን አቁሞ ቀና ብሎ አያት። ቆዳዋ ተገልቧል፣ ከርቀት ጠቆር
ብለ የታየው አካሏ ቁልቁል ወደሱ ሲመጣ እየጎላ ታየው። የራቀው
ሽለቆ ቀረበው።
ንጥት ያለው ገላዋ በተለይም ጭኗን ትክ ብሎ እያዬ፡ “ካርለትት አላትና አይኖቹ ሳቁ። ሃይል ያጣችው ካርለት
የተሸበሸበ ርጥብ ከንፈሯን ለጠጥ አርጋ ደካማ ፈግታዋን አሳየችው።
ባለወይሳው አስተውሎ አያት ውስጧንም አየው
የተቀጣጠለውን ስሜቷን ነካው፡
ጭኖቹ ላይ ያለውን ወይሳ አንስቶ ለጨረቃ ሰጣት!
ጨረቃም ወይሳውን ተቀብላ እየነፋች ጥዑም ዜማዋን ማንቆርቆር ጀመረች። በጨረቃ የሙዚቃ ቃና ደልቲ ቀኝ እጁ እየተንከላወሰ ወደ
ነጩ ጭኗ ገባ። ነዘራት
በሽተኛዋን! “በሽታውን የደበቀ..." እንዲሉ እሷም ሃኪሟን ረዳችው የሚያቃጥላትን የሚቆረጥማትን እጁን
በእጅዋ ይዛ አሳየችው።
ጆሮ ግንዱን ፀጉሩን
ማጅራቱን...እየደባበሰች የእርዳኝ ጥሪዋን አሰማችው። ሀኪሟ በስሜቷ እሱም ተሽፈነ። ለጋራ በሽታቸው ግን የሚበጀውን ያውቃል። ስለዚህ ማገገሚያ ቀንዱን አቁሞ ይዞ ከተቀመጠበት ተነሳ።
ሙዚቃው ይስረቀረቃል! ዳንሱ ጦፏል... ጨረቃ
ታዜማለች ! ቅጠሉ እስክስታ ይወርዳል! ነፋሱ አታሞውን
ይደልቃል... ጥቁርና ነጭ ቀለሙ ማራኪ ዜብራም ያናፋል...
ኮንችት ጭፈራውን በጉጉት እያየች እንደቆየች ስለ ነገው
ጉዟቸው ካርለትን ለመጠየቅ ፈልጋ አጣቻት የኩችሩ መንደር ኗሪ
ጥበቃውን አላቆመም። ነጩ እባብና ሎካዬ ግን አልመጡም። ኮንችት
በየዋህነታቸው ብታዝንም ማድረግ የምትችለው ባለመኖሩ በዝምታ
ሁኔታውን ስትከታተል ሰነበተች። የመቆያ ፈቃዷ እያለቀ ነው:: ስፔን ስትመለስ ብዙ ልትሰራ አስባለች በተለይ ስለ ኢትዮጵያ ስለ ኩጉዩ፡ ከመሄዷ በፊት ግን ሐመርን ኤርቦሬን ከካርለት ጋር በሷ
መኪና ለማየት ተስማምታለች ጉዞዋን በተመለከተ ግን ከካርለት
ጋር መነጋገር ያለባት ቁም ነገር ነበር።
ኮንቺት ካርለትን ስታጣት ደልቲን በጨረቀዋ ብርሃን ፈለገችው የለም:
ካርለት የሄደችው እሱ ዘንድ ይሆን?' አብረው ሆነው
ለማየት ጓጓች: ፍቅር ሲለዋወጡ እንዴት ይሆን?' ለማስብ ሞከረች:: መልሳ ደግሞ ሃጢያት እንደሰራች ሁሉ አስበችው አፈረች። ሆኖም ግን አልቻለችም ጉጉቷ ጨመረ።
በዚህ መካከል ድክምክም ያለውን የወይሳውን ድምፅ
ኮንችት ከርቀት ሰማችው። በድፍረት ሄደች ወደ ጫካው! ድንገት ግን ክው ኦለች ! ባለበት የሚሰግር
ዜብራ አየች ፈራችው
ዜብራውን ይጋልባል ... በስሜት ተውጣ አይኖችዋን ጨፈነች:
"...የፍቅር እንጥሌን ሌሎች ተንጠራርተው ሲያጡት የነካው እሱ ብቻ ነው" ኮንችትን የነገረቻት ትዝ አላት።
“ዋው! ጎመጀች በዜብራው
ግልቢያውን አሰጋገሩን
አደነቀችው። ወደደችው ያን ስሜት ሰላቢ ጥዑም ዜማ... ፈውስ ሰጭ ዳንኪራ… ንፁህ የጫካ ፍቅር... ማራኪ ተፈጥሮ ተጋግዘው እንግዳዋን መልሀቋን አስጥለው በጉጉት ገተሯት! ተጣራች በሲቃ ሶራ ግን አልሰማትም! ኤጭ! ብላ ከንፈሯን ጣለች። ጎደሎነት
ተሰማት ያማራትን የዜብራ ግልቢያ ግን የሚያቀምሳት አጣች.የጎመጀችለትን ያጣችው ኮንችት አዘነች። ...ዛፉ ቅጠሉም አዘነላት ላልተጠራችው ተመልካች!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“እ. እ..." አቃሰቱ እምቡዋ እ. እ" ሳግ ተናነቃቸው
ህፃናት ወጣቶች አዛውንቶች ኦሞ ወንዝ ዳር ጫካ ተሰባስበው እንግዶች በእንጨቷ ታንኳ ኦሞን ሲያቋርጡ አያቸው።
ኮንችት እጅዋን አውለበለበችላቸው “ቻው... ባባይ... አለቻቸው። ዝም አሉ ኩዩጉዎች የነሱ የጥልቅ ፍቅር መግለጫቸው ዝምታ ነው። ሳግ ያበት “እ... እ..." እሚያሰኝ ከጥጃዋ በሃይል እንደተነጠለች ላም የሚያንሰፈስፍ ዝምታ! “እ. እ. እምቡዋ.. እያሰኘ የማይፈስ እንባ የሚያስነባ, የማይገልፁት ግን የሚታይ
የሚነካ... የመለየት ጭንቀት የሚታይበት ስሜት..
“እወዳችኋለሁ! ከናንተ በመለየቴ አዝናለሁ. ምንጊዜም አልረሳችሁም..." ኮንችት በስፓኒሽ ለመግለፅ ለፈለፈች¦ ምላሽ ግን
አልነበረም። “ፀጥታ ብቻ! ለኩዩጉዎች የመለየትን መጥፎነት የሚገልፅ ቋንቋ የላቸውም ካለ ዝምታ በቀር።
ኮንችት አነባች::
የካርለትን ትከሻ ተደግፋ አነባች አለቀለች ሌሎች ግን ዝም ረጭ ብለዋል እንደ ሌሎች ወንዞች
የማይጮኸው የማይደነፋው.
የኩዩጉዎች ህይወት የመልክ ማያ መስታዋታቸው የሆነው የኦሞ ወንዝም በዝምታ ድባብ እንደ ተዋጠ
ነው: ወፎች ግን ይበራሉ ያዜማሉ! እዕዋት ያሽበሽባሉ...
“እሷ ሄደች በሉ
ሉካዬንና የሰላም አድባራችን
የነበረውን ነጩን እባብ እንጠብቅ ! ተከፍተን ታዩን መምጣቱን እንዳይተዉት እንዝፈን እንጫወት.."
ሽማግሌዎች ለኩችሩ መንደር ህዝባችው ተናገሩ ኮንችት ካርለት ከሎ ሶራ… ኦሞን ከተሻገሩ በኋላ ዞር ብለው አዩ: ኩዩጉዎች የሉም!.ሲደልቁ ግን ይሰማል ለዚህች ተለዋዋጭ ዓለም ለረጅም ጊዜ አልቅሶና አዝኖስ መኖር እንዴት ይቻላል!
👍26❤3👎1🥰1😁1
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከእንቅልፉ ረፋዱ ላይ ነቃ ክፍሉ በብርሃን ተሞልቷል
እንደተጋደመ ማሰብ ጀመረ ተስፋ ያለው ነገር አልታየውም እዚች
አገር ከመኝታው ሲነቃ ፍንድቅድቅ የሚል የእናቱን ጡት የሚጠባ ህፃን ብቻ ነው" ሌላው ግን ህሊናውን እያከከ ምን ሰርቶ እንደሚበላ ያስባል፤ ምን ሰርቶ እንደሚኖር ያልማል ትንሹ በትልቁ ህሊና
ገብቶ መሞትን ይመኛል ሞት የሌለበትን አሸናፊነት ለማግኘት ይማስናል እና ከመኝታው ሲነሳ ጭንቀትንና ተስፋ መቁረጥን ያዛጋል
ምነው አገሬ ጭንጫ ምድር በሆነች ኖሮ ለፋን ለፋን
ምርት ግን ጠፋ ብለን እናመሃኝ ነበር ምነው ከርሰ-ምድሯ በደረቀ
ኖሮ ካለውሃ መቼስ ምን መስራት ይቻላል እንልም ነበር ካላት የከርሰ-ምድር ውሃ አስር ፐርሰንት እንኳ አለመጠቀሟን ባናውቅ
ምነው የሰው ኃይልስ ባልኖረ ምን ይደረግ
የአለንን ለመጠቀም
ሰው ያስፈልጋል እንልም ነበር የሰው ኃይል ባልኖረ ኖሮ ይህች አገር ግን ሁሉም አላት ልምላሜ ታሪክ ውበት እህ!.. የጭንቀታችን ምንጭ የሆነው ህምታ ከየት መጣ?" የእኛ ትውልድ የወሲብ የጦርነት የዝርፊያ ፊልም ማየት በቃው? እኮ ምን አለፋን በፊልም የሌለንን እናያለን በፊልም የማንኖረውን እንኖራለን ..." ብሎ ሲፈላሰፍ ቆይቶ
ከመኝታው አፈፍ ብሎ ተነሳና ወደ ተናኘ መኝታ ክፍል ሄደ ተናኘ በጠዋቱ የለችም እሱ ግን ወደ አልጋዋ ተጠጋና ጠርዙ ላይ ቁጭ አለ ራስጌዋ ካለችው ትንሽ ኮመዲኖ ላይ የእለት ውሎዋን የምትፅፍበትን ማስታወሻ አየው" ላንሳው አላንሳው ከህሊናው ጋር
ተሟገተ እረፍ እረፍና ተነስ! ህሊናው አዘዘው"
እንጃባህ! በልጄ …'
"ኦሆሆ! ጅል አትሁን አንተ አባት ማስታወሻ ደግሞ
ምሥጢር ተቀባይና አስቀማጭ ነው" አንተን አያውቅም ለአንተም
አይታዘዝም ጌታው እሷ ናት ገላጯ ፀሐፊዋ ልጅህ ናት
ለአንተ የሚሆነውን ከእሷ ጠይቅ ከእሷ ህሊና አንብብ
"ማንም ሰው ሊገልፀው የማይፈልግ የምሥጢር መቃብር ህሊናው ውስጥ አለ በሐዘን ብቻውን እንደ ጥጥ ተባዝቶ አስከፊ
መቃብሩን ተሸክሞ በፍርሃት እየራደ ከአፅም ጋር እየተፋጠጠ እጣ ፋንታው የሆነውን ዘግናኝ ህይወቱን የሚኖር አለ! ... የህሊና ውስጥ ሞት ሃዘንተኛ የማይጠይቅበት የመቃብር ሐውልት የማይታነፅበት
በየግላችን ያጣነውን መልካምም ሆነ መጥፎ የህይወት እጣ በሙሚ
ቀባብተን ሳይበሰብስ የምንቀብርበት ብቸኛው የመቃብር ሥፍራ
ህሊናችን ነው" ሁለተኛ የመቃብር ሥፍራ ደግሞ የግል ማስታወሻ
ነው" ማንም ሊያየው፥ ሊመራመርበት ሊጎበኘው ... አይችልም
ካለባለቤቱ በስተቀር ለሌላ ሰው ዝግ ነው ስለዚህ ማስታወሻዋን
አትንካው ! በሃጢያት ደም ህሊናህን አትበክለው ...'
አያገባህም፤ ለልጄ ከኔ የበለጠ ምሥጢር ጠባቂ የላትም ይህን ሲያስብ ሰቀጠጠው፤
"እሽ ልጄ የራሷ የህይወት ምሥጢር ይኖራት ይሆናል
ማወቅም አይገባኝ ይሆናል ማስታወሻዋን ማንበቤም ትልቅ የህሊና ወቀሳ ያመጣል" ግን እሷን ደግሞ ማወቅ አለብኝ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ አስፈልጋታለሁ አለሁልሽ የማልላትን ልጄን እውነተኛ
እሷነቷን በመጠየቅ አላገኘውም የማነበው ልቆጣጠራት አይደለም
ለዚያማ ህሊናዋ የት ሄዶ የምታነበው መጽሐፍ መች አንሷት እሳትና ውኃ
ለልጄ ማወቅ ያለባትን ማሳወቅ የነበረብኝንም እሳትና ውኀ
አሳይቻታለሁ እንዴት እንደምትጠጣና እንደምታበስል ግን እያየች፥
እያነበበች እየሞከረች
ተማረች አባት ልጁን ዘለዓለም የሚያስተምር መምህር አይደለም ትምህርት አያቆምም አባትና የክፍል አስተማሪ ግን የማስተማሩ እድላቸው የሆነ ደረጃ ላይ ያቆማል ከዚያ መማማር በመጨረሻ ደግሞ ይማራሉ" እና!- ከልጄ የህይወት ፈተና ልማር ተወኝ" ብሎ ህሊናውን መንጭቆት
ማስታወሻዋን ከኮሞዲኖው ላይ አነሳው
ሰርቶ መብላት ምን ነውር አለው መሰደድስ ቢሆን
ወንድማለም! ከቸገረህ ምን ያሳፍራል? እውነቴን'ኮ ነው በሃብት ደልበዋል የተባሉትስ አሜሪካኖችና አውሮፓውያን ተሰደው ለአረብ አሽከር ሆነው ብራቸውን አፍሰው አገራቸው ይገቡ የለ ..." የሚለውን የራስ ማፅናኛ አባባል አንብቦ ሌላ ገፅ ገለጠ።
"ወንድማለም! ወገቤ እስኪቆረጥ ለሰዓታት ስማስን ቀኑ ነጉዶ
ለሊቱ ጭላጭ ሰዓት እየቀረው ነው ምስጋና የሌለበት ባዶ ህይወት!
“ለገንዘብሽ ነው ስትቆይ ያው መጥገብሽ አይቀርም ፀባይሽ ካላማረ ኮንትራትሽን ሰርዞ መተካት ነው ተሰልፎ ከሚለምነው አንዱን
እየተባልህ የዕቃ ክብር ተነፍጎህ በዘመናዊ ባርነት መኖር ወንድማለም ደከመኝ እባክህ ልተኛ! ልተኛ ማን አስተኝቶኝ ባለቤቷ እንቅልፍ ስታጣ የኔን መኝታ በር አንኳኩታ ቀስቅሳኝ
ተመልሳ መተኛት ልማዷ ነው" አንዳንዴ ሳስበው እኔ ሰራተኛዋ ብቻ ሳልሆን የእንቅልፍ ማስወሰጃ እንክብሏም ነኝ እላለሁ በል
ለሁሉም ጎኔን ላሳርፈው ማለቱ ይሻለኛል የሚለውንም አንብቦ ሌላ
ገፅ ገለጠ።
"አይ ወንድማለም! ይሄንስ እድሜ ልክህን ባታስበው
ይሻላል" ለአንተ እኔ ሁሌ ህፃን ነኝ አይደል? ግንኮ ህፃን ከሆንኩ ሁለት አስርተ ዓመታት አለፉ ግን አንተ ስለጎረምሳነት ዘመንህ
ለምንድን ነው የማታወራው? የምትወደድ ሰው ነበርህ? ወይንስ
ጨካኝ: ዋሾ! ... ሁሉንም ሁን ለምን እንደሆንህ አላውቅምና ጭፍን
ያለ የተሳሳተ ፍርድ ሰጥቼ ልወቅስህ አልሻም ያ አይነት ፍርድ መስጠት ካቆምሁ ደግሞ ቀናት ተቆጠሩ።
"ወንድዬ! የጀመርሁትን ሳልነገርህ ምን ዙሪያ ጥምጥም አዞረኝ? ማስታወሻዬን ነው አታነበው፤ግን ፈራሁህ ስፅፍ እያሰብሁህ ነው" በዚህ ዓለም የምታምኝው?'
ብባል የለኝም
የምትቀርቢው? ከተባልሁ
ግን ወንድማለምን
ነው የምለው"ይከፋህ ይሆን? ይክፋህ እንጂ የምወድህ
ስለማላምንህ ስንት የደበቅሁህ ጉድ አለ መሰለህ አንተ መቼም እንደ
አባቴ ብትሆንም
ብዙ አባቶች ድፍን ፍቅርን የምትሻ ግብዝ አባት አትመስለኝም ሁሉም ልክ እንዳለው ታውቃለህ አይደል?"
"ፍቅሬ አገረሼ ወንድዬ! አንድ ጊዜ በየሄድሁበት እያስነጠሰ የሚያሳጣ ፍቅር ይዞኝ ነበር" ያ የፍቅር ገጠመኝ አሁን ተረት ነው
የነ ጦጢትና አንበሳ ተረት የዓረብ ቤት እያፀዳሁ ግን ያ የተረት ስሜቴን ፏጨረው፤ አንዴ ይቆረጥመኛል ሌላ ጊዜ ይለበልበኛል እንደ ቁርጠት ቀስፎ አላስቆም አላስቀምጥ ይለኛል
ያንጠራራኛል እንደ ምጥ ገፍቶ ሲመጣ ደግሞ ሲቃ ነው፡ ውለጂው ነው
አንተ ወንድማለም! አሁን አሁን ሳስበው ከሱስ ነፃ ነኝ!' እያልሁ ስመፃደቅ ለካ ማፍረሻ የሌለው ሱስ ሱሰኛ ነኝ እህህህ በሱስ መጠመድ ቢሉህ መጠመድ ነው ያውም በቅርብ ባላረከው
ወደፊትም በቅርቡ በማታገኘው ሱስ የሚፋጨው የስሜት ስለት
ህሊናህን ሲበሳሳው፤ እየወጠረ ሲያከረው ነፍስህ ረፍት አጣ ውጪ
ነፍስ ግቢ ነፍስ ብትሰቃይ ምን ይሰማህ ይሆን?" ፈገግ አለ ጥያቄዋ
አፈፍ አድርጎ ተሸክሞት ወደ ኋላው ከነፈ አልፎት ወደመጣው የወጣትነት ህይወት የልጁን ምስጢር ከዚያ በላይ አንብቦ ማወቅ
ግን አልፈለገም እሷ ግን ማስታወሻዋ ላይ ስሜቷን: ውጥረቷን ረሃቧን ጥማቷን ... ዘክዝካው ነበር"
"... ወንድማለም የአለሁት ወህኒ ቤት ነው ትናንት ሃያ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከእንቅልፉ ረፋዱ ላይ ነቃ ክፍሉ በብርሃን ተሞልቷል
እንደተጋደመ ማሰብ ጀመረ ተስፋ ያለው ነገር አልታየውም እዚች
አገር ከመኝታው ሲነቃ ፍንድቅድቅ የሚል የእናቱን ጡት የሚጠባ ህፃን ብቻ ነው" ሌላው ግን ህሊናውን እያከከ ምን ሰርቶ እንደሚበላ ያስባል፤ ምን ሰርቶ እንደሚኖር ያልማል ትንሹ በትልቁ ህሊና
ገብቶ መሞትን ይመኛል ሞት የሌለበትን አሸናፊነት ለማግኘት ይማስናል እና ከመኝታው ሲነሳ ጭንቀትንና ተስፋ መቁረጥን ያዛጋል
ምነው አገሬ ጭንጫ ምድር በሆነች ኖሮ ለፋን ለፋን
ምርት ግን ጠፋ ብለን እናመሃኝ ነበር ምነው ከርሰ-ምድሯ በደረቀ
ኖሮ ካለውሃ መቼስ ምን መስራት ይቻላል እንልም ነበር ካላት የከርሰ-ምድር ውሃ አስር ፐርሰንት እንኳ አለመጠቀሟን ባናውቅ
ምነው የሰው ኃይልስ ባልኖረ ምን ይደረግ
የአለንን ለመጠቀም
ሰው ያስፈልጋል እንልም ነበር የሰው ኃይል ባልኖረ ኖሮ ይህች አገር ግን ሁሉም አላት ልምላሜ ታሪክ ውበት እህ!.. የጭንቀታችን ምንጭ የሆነው ህምታ ከየት መጣ?" የእኛ ትውልድ የወሲብ የጦርነት የዝርፊያ ፊልም ማየት በቃው? እኮ ምን አለፋን በፊልም የሌለንን እናያለን በፊልም የማንኖረውን እንኖራለን ..." ብሎ ሲፈላሰፍ ቆይቶ
ከመኝታው አፈፍ ብሎ ተነሳና ወደ ተናኘ መኝታ ክፍል ሄደ ተናኘ በጠዋቱ የለችም እሱ ግን ወደ አልጋዋ ተጠጋና ጠርዙ ላይ ቁጭ አለ ራስጌዋ ካለችው ትንሽ ኮመዲኖ ላይ የእለት ውሎዋን የምትፅፍበትን ማስታወሻ አየው" ላንሳው አላንሳው ከህሊናው ጋር
ተሟገተ እረፍ እረፍና ተነስ! ህሊናው አዘዘው"
እንጃባህ! በልጄ …'
"ኦሆሆ! ጅል አትሁን አንተ አባት ማስታወሻ ደግሞ
ምሥጢር ተቀባይና አስቀማጭ ነው" አንተን አያውቅም ለአንተም
አይታዘዝም ጌታው እሷ ናት ገላጯ ፀሐፊዋ ልጅህ ናት
ለአንተ የሚሆነውን ከእሷ ጠይቅ ከእሷ ህሊና አንብብ
"ማንም ሰው ሊገልፀው የማይፈልግ የምሥጢር መቃብር ህሊናው ውስጥ አለ በሐዘን ብቻውን እንደ ጥጥ ተባዝቶ አስከፊ
መቃብሩን ተሸክሞ በፍርሃት እየራደ ከአፅም ጋር እየተፋጠጠ እጣ ፋንታው የሆነውን ዘግናኝ ህይወቱን የሚኖር አለ! ... የህሊና ውስጥ ሞት ሃዘንተኛ የማይጠይቅበት የመቃብር ሐውልት የማይታነፅበት
በየግላችን ያጣነውን መልካምም ሆነ መጥፎ የህይወት እጣ በሙሚ
ቀባብተን ሳይበሰብስ የምንቀብርበት ብቸኛው የመቃብር ሥፍራ
ህሊናችን ነው" ሁለተኛ የመቃብር ሥፍራ ደግሞ የግል ማስታወሻ
ነው" ማንም ሊያየው፥ ሊመራመርበት ሊጎበኘው ... አይችልም
ካለባለቤቱ በስተቀር ለሌላ ሰው ዝግ ነው ስለዚህ ማስታወሻዋን
አትንካው ! በሃጢያት ደም ህሊናህን አትበክለው ...'
አያገባህም፤ ለልጄ ከኔ የበለጠ ምሥጢር ጠባቂ የላትም ይህን ሲያስብ ሰቀጠጠው፤
"እሽ ልጄ የራሷ የህይወት ምሥጢር ይኖራት ይሆናል
ማወቅም አይገባኝ ይሆናል ማስታወሻዋን ማንበቤም ትልቅ የህሊና ወቀሳ ያመጣል" ግን እሷን ደግሞ ማወቅ አለብኝ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ አስፈልጋታለሁ አለሁልሽ የማልላትን ልጄን እውነተኛ
እሷነቷን በመጠየቅ አላገኘውም የማነበው ልቆጣጠራት አይደለም
ለዚያማ ህሊናዋ የት ሄዶ የምታነበው መጽሐፍ መች አንሷት እሳትና ውኃ
ለልጄ ማወቅ ያለባትን ማሳወቅ የነበረብኝንም እሳትና ውኀ
አሳይቻታለሁ እንዴት እንደምትጠጣና እንደምታበስል ግን እያየች፥
እያነበበች እየሞከረች
ተማረች አባት ልጁን ዘለዓለም የሚያስተምር መምህር አይደለም ትምህርት አያቆምም አባትና የክፍል አስተማሪ ግን የማስተማሩ እድላቸው የሆነ ደረጃ ላይ ያቆማል ከዚያ መማማር በመጨረሻ ደግሞ ይማራሉ" እና!- ከልጄ የህይወት ፈተና ልማር ተወኝ" ብሎ ህሊናውን መንጭቆት
ማስታወሻዋን ከኮሞዲኖው ላይ አነሳው
ሰርቶ መብላት ምን ነውር አለው መሰደድስ ቢሆን
ወንድማለም! ከቸገረህ ምን ያሳፍራል? እውነቴን'ኮ ነው በሃብት ደልበዋል የተባሉትስ አሜሪካኖችና አውሮፓውያን ተሰደው ለአረብ አሽከር ሆነው ብራቸውን አፍሰው አገራቸው ይገቡ የለ ..." የሚለውን የራስ ማፅናኛ አባባል አንብቦ ሌላ ገፅ ገለጠ።
"ወንድማለም! ወገቤ እስኪቆረጥ ለሰዓታት ስማስን ቀኑ ነጉዶ
ለሊቱ ጭላጭ ሰዓት እየቀረው ነው ምስጋና የሌለበት ባዶ ህይወት!
“ለገንዘብሽ ነው ስትቆይ ያው መጥገብሽ አይቀርም ፀባይሽ ካላማረ ኮንትራትሽን ሰርዞ መተካት ነው ተሰልፎ ከሚለምነው አንዱን
እየተባልህ የዕቃ ክብር ተነፍጎህ በዘመናዊ ባርነት መኖር ወንድማለም ደከመኝ እባክህ ልተኛ! ልተኛ ማን አስተኝቶኝ ባለቤቷ እንቅልፍ ስታጣ የኔን መኝታ በር አንኳኩታ ቀስቅሳኝ
ተመልሳ መተኛት ልማዷ ነው" አንዳንዴ ሳስበው እኔ ሰራተኛዋ ብቻ ሳልሆን የእንቅልፍ ማስወሰጃ እንክብሏም ነኝ እላለሁ በል
ለሁሉም ጎኔን ላሳርፈው ማለቱ ይሻለኛል የሚለውንም አንብቦ ሌላ
ገፅ ገለጠ።
"አይ ወንድማለም! ይሄንስ እድሜ ልክህን ባታስበው
ይሻላል" ለአንተ እኔ ሁሌ ህፃን ነኝ አይደል? ግንኮ ህፃን ከሆንኩ ሁለት አስርተ ዓመታት አለፉ ግን አንተ ስለጎረምሳነት ዘመንህ
ለምንድን ነው የማታወራው? የምትወደድ ሰው ነበርህ? ወይንስ
ጨካኝ: ዋሾ! ... ሁሉንም ሁን ለምን እንደሆንህ አላውቅምና ጭፍን
ያለ የተሳሳተ ፍርድ ሰጥቼ ልወቅስህ አልሻም ያ አይነት ፍርድ መስጠት ካቆምሁ ደግሞ ቀናት ተቆጠሩ።
"ወንድዬ! የጀመርሁትን ሳልነገርህ ምን ዙሪያ ጥምጥም አዞረኝ? ማስታወሻዬን ነው አታነበው፤ግን ፈራሁህ ስፅፍ እያሰብሁህ ነው" በዚህ ዓለም የምታምኝው?'
ብባል የለኝም
የምትቀርቢው? ከተባልሁ
ግን ወንድማለምን
ነው የምለው"ይከፋህ ይሆን? ይክፋህ እንጂ የምወድህ
ስለማላምንህ ስንት የደበቅሁህ ጉድ አለ መሰለህ አንተ መቼም እንደ
አባቴ ብትሆንም
ብዙ አባቶች ድፍን ፍቅርን የምትሻ ግብዝ አባት አትመስለኝም ሁሉም ልክ እንዳለው ታውቃለህ አይደል?"
"ፍቅሬ አገረሼ ወንድዬ! አንድ ጊዜ በየሄድሁበት እያስነጠሰ የሚያሳጣ ፍቅር ይዞኝ ነበር" ያ የፍቅር ገጠመኝ አሁን ተረት ነው
የነ ጦጢትና አንበሳ ተረት የዓረብ ቤት እያፀዳሁ ግን ያ የተረት ስሜቴን ፏጨረው፤ አንዴ ይቆረጥመኛል ሌላ ጊዜ ይለበልበኛል እንደ ቁርጠት ቀስፎ አላስቆም አላስቀምጥ ይለኛል
ያንጠራራኛል እንደ ምጥ ገፍቶ ሲመጣ ደግሞ ሲቃ ነው፡ ውለጂው ነው
አንተ ወንድማለም! አሁን አሁን ሳስበው ከሱስ ነፃ ነኝ!' እያልሁ ስመፃደቅ ለካ ማፍረሻ የሌለው ሱስ ሱሰኛ ነኝ እህህህ በሱስ መጠመድ ቢሉህ መጠመድ ነው ያውም በቅርብ ባላረከው
ወደፊትም በቅርቡ በማታገኘው ሱስ የሚፋጨው የስሜት ስለት
ህሊናህን ሲበሳሳው፤ እየወጠረ ሲያከረው ነፍስህ ረፍት አጣ ውጪ
ነፍስ ግቢ ነፍስ ብትሰቃይ ምን ይሰማህ ይሆን?" ፈገግ አለ ጥያቄዋ
አፈፍ አድርጎ ተሸክሞት ወደ ኋላው ከነፈ አልፎት ወደመጣው የወጣትነት ህይወት የልጁን ምስጢር ከዚያ በላይ አንብቦ ማወቅ
ግን አልፈለገም እሷ ግን ማስታወሻዋ ላይ ስሜቷን: ውጥረቷን ረሃቧን ጥማቷን ... ዘክዝካው ነበር"
"... ወንድማለም የአለሁት ወህኒ ቤት ነው ትናንት ሃያ
👍29
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
የወሮ መንደር ሽማግሎች ከሁለቱ መንደሮች መሃል ካለችው ትንሽ ሜዳ ግማሽ ክብ ሰርተው በርኮታቸው ላይ ተቀምጠዋል" ባለ
ጴሮው፥ ሹልሹላው፥ የሰጎን ላባ ፀጉሩ ላይ የሰካው ሁሉም በተመስጦ ስብሰባው እስኪጀምር ለውይይቱ ህሊናቸውን ይሳስላሉ ህፃናት ከሽማግሎች ርቀው
እንቧይ እየተቀባበሉ
ይጫወታሉ ጋልታምቤ ከቤቱ ወደ ሜዳው በምትወስደው ቀጭን ጎዳና ሄዶ ከሽማግሎች ጋር ተቀላቀለ ሌሎችም ከያቅጣጫው እየመጡ
ተደባለቁ„
ረጅም ጦር የያዙት የመንደሩ አለቃ (ዘርሲ) ከተቀመጡበት
ተነሱና ከወገባቸው ከታጠቁት ዝናር ጩቤ አውጥተው ጎረምሶች
የያዙትን ለፍላፊ ፍየል በቁሙ ጉሮሮው ላይ ወጉትና ፍየሉ ሲወድቅ
ከደሙ ጦራቸው ላይ ከፈርሱ ደግሞ ባታቸውን ቀባ-ቀባ አድርገው
ሄድ መለስ: ሄድ መለስ ብለው ንግግር ጀመሩ
"ጥሩ ነው! ዝናቡ መጥቷል መሬቷ ሳር አብቅላለች፥
ተራሮች እንደ ልጃገረድ አጊጠዋል ድንጉላ ቢራቢሮዎች፥ ወፎች
ይበራሉ" ንቦች አበባቸውን እየቀሰሙ ወደ ቀፎቻችን ይተማሉ፥ ውሃ የጠማት ምድር እምትጠጣው አግኝታለች እኛም የምንጠጣውን ከስኬ ይሰጠናል አሸዋውን ስንጭረው ውሃ መሬቷን በጧር ስንወጋት ማሽላ እናገኛለን ዳመናውን ሰርስራ
በምትወጣው ጨረቃም ልጆቻችን ይደሰታሉ
እንግዲህ ተቀያችን: ከዚች
አባቶቻችን ካቆዩን ምድር ምን ጎደለ!" ብለው ዝም አሉ የሽማግሎች
አለቃ" እንደገና ሄድ መለስ እያሉ ሁሉንም በዐይናቸው እየቃኙ
ብዙዎቹ ተሰብሳቢዎች ዐይናቸው ያለው ሌላ ቦታ ነው ሐመር ላይ ነገር በዐይን አይገባም' ነገር የሚደመጠው በልቦና ነው፤
ልቦና ያያል ልቦና ይሰማል
ልቦና ይመራመራል ልቦና
ይወስናል" በልቦና ለማየትና ለመስማት ግን ፀጥታ ያስፈልጋል ውስጣዊ እርጋታ የሃሳብ ማዕበል የሌለበት መተራመስ የተረጋጋበት ሊሆን ይገባል" ሐመር ላይ ሽበት ብቻ
ለሽምግልና አያበቃም፤
ጀግንነት ብቻ አያስከብርም
ማህበራዊ ችግርን ለመፍታት በጥንቃቄ ውሉን ፈልጎ አግኝቶ ትብትቡን
የሚፈታ ህሊናው ቀልጣፋ ከጀግንነቱም ከፍርድ አዋቂነቱም ሁለገብ ችሎታ ያለው መሆን ያሻል ለሽምግልና ለመታጨት
"ጥሩ ነው! የአባቶቻችን መንፈስ ከእኛ ጋር አለ እንዳንራብ መከራ እንዳይበዛብን ዝንጉ እንዳንሆን የነሱ መንፈስ እንደ ዛፍ ጥላ ከለላ ይሆነናል ይሁን እንጂ በአባቶቻችን የነበረው ችግር አሁንም
አለ አሁንም የአባት ጠላት አለን አሁንም የአባት ጠላቶች እያዘናጉ የከብቶቻችንን ጅራት ሊጎትቱ የሚስቶቻችንን እጅ ሊስቡ፥ የላሞቻችንን ጡት ሊያልቡ ይፈልጋሉ ተናጋሪው ንግግራቸውን ገተው ዙሪያ ገቡን እያዩ ፀጥ አሉ የኦሞ ወንዝ ቆሞ ያውቃል? ውሃ ታግዶ ይቆማል? ያባት
ደንብም እንዲሁ ነው፤ ሁሌም ከልጅ ወደ ልጅ ግድቡ በሽማግሎች
እየተከፈተ ከላይ እየወረደ የመጣው ወደሚቀጥለው
ትውልድ እየቶንዶለዶለ
ይፈሳል" ለዚህ ነው ከስኬ ሲጫር ውሃ: የእኛ ልብ
ሲቆፈር ደግሞ ያባት ደንብና ባህል የሚፈልቀው፤ ከእኛ መሃል ልቡ ሲቆፈር የአባት ደንብና ባህል የማያፈልቅ ደረቅ ካለ ግን ከጠላት
የተወረወረብን ድንጋይ ስለሆነ አምዘግዝገን መወርወር፥ ካካባቢያችን
ማጥፋት ይኖርብናል" ተናጋሪው ሽማግሌ ንግግራቸውን ገትተው
የተናገሩትን እንደገና በህሊናቸው አጣጣሙት።
"ወንድሞቼ የአባቶቻችን መንፈስ ከእኛ ጋር ነው
የምንሰራውን እነሱ ካቆዩን ደንብ ጋር ካላመዛዘነው እንደ ዱር ጉንዳን ማን እንደቆመብን ሳይታወቅ፤ ምንነታችንም ሳይጠየቅ አውራ እንደሌለው የሚያስተባብረው እንዳጣ ንብ በየጢሻው እንበተናለን
እንጨት ቆርጠን ሳር አጭደን ለንብ ቀፎ እየሰራን: እኛ ግን ተሰርቶ የቆየንን የአባት ደንብ ደህንነቱን
በመጠበቅ ለልጅ ልጆቻችን ማስተላለፍን ዘንግተናል" ከጉንዳን: ከንብ አንሰን የአባት ደንብ እየሻርን ነው: ትብብራችን እየላላ ነው፥ ወኔያችን ተሸንቁሮ
ንፋስ እየገባው ነው." እንደገና ቃኙት ተሰብሳቢውን በዝምታ።
"አውሬ ይሁን ወፍ የማይታወቅ ጉድ በአራት እግሩ መንደራችን እየመጣ ሲቆም በሰፊው ሆዱ ሴቶቻችንን እየሸፋፈኑ
እያቀፈ ሲወስድና ሲመልስ
ሴት ልጅ ወንድ የዘራውን ማብቀል ሲሳናት እኛ አልተቃወምንም! ኧረ ተው! የተቀበልነውን የማናቀብል ጅብ አንሁን ጅብ የሚኖረውና የሚሞተውም ለሆዱ ነው የአባት ደንብ የለው ለልጄ ማለት አያውቅ አፍንጫው ጥንብ እንዳሸተተ: ሆዱ ለመብላት እንደተስገበገበ
ኖሮ ይሞታል ለልጄ ሳይል ደንብ ሳይኖረው ጥንብ እንደ አማተረ ይሞታል ለሆዱ! የተናጋሪውን ሃሳብ ከሚያዳምጡት መካከል አንዱ ሽማግሌ
የዘርሲዎች አለቃ በተናገሩ ቁጥር "ህም ህም… "አሉ በሐመር የስብሰባ ደንብ አንዱ ሲናገር ሌላው ህም ህም ካለ ልቀጥል ልናገር ማለት ስለሆነ የሽማግሎች አለቃ የንግግር እድሉንና
ተናጋሪው የሚይዘውን ጦር አቀበሉ ተረኛው ሽማግሌ ጦሩን በቀኛቸው ይዘው ከፍየሉ ፈርስ ባታቸውንና ግንባራቸው ቀባ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ሽማግሎችን: ህፃናትን: መንደሩን: ዙሪያ
ገቡን ቃኙት ጦሩ እጃቸውን ነዘረው ስሜታቸውን በሙቀቱ አጋጋለው፤ ወኔያቸውን እንደ ብረቱ ጫፍ አጠነከረው የአያት
የአባቶቻቸው መንፈስ ከጦሩ ተነስቶ ወደ ልቦናቸው ተስለከለከ
ጥሩ ነው! የቀጋ ፍሬ ከሾላ ዛፍ የለቀመ ማነው ሾላና
ቀጋን ደባልቆ የሚበላ ግን አስተዋይ ነው ይህ ሰው የተፈጠረው ደግሞ እዚሁ እኛ ዘንድ ቡስካ ተራራ ላይ ነው ያ ሰው እሳት
አንድዶ የሚፈልጋቸውን መልካም መልካም ሰዎች በእሳት ብርሃን
ከያካባቢው ጠራቸው
እንግዲህ አያቶቻችን የባንኪሞሮን እሳት
እያዩ ከያቅጣጫው የተሰባሰቡ ናቸው እኒያን ፍሬዎች ቀጋና ሾላዎች ባንኪሞሮ ደባልቆ በሐመር ምድር በተናቸው"
አያቶቻችንና አባቶቻችን በቀሉ ከእኒያ ብሩክ ፍሬዎች ደግሞ እኛ በቅለን እህ! በተራችን እንድናፈራ ላደረጉን አባቶቻችን ውለታችን ምንድነው?" ብለው ዝም አሉ ሽማግሌው በጠየቁት ጥያቄ አንጀታቸው እየተላወሰ መልሱን ግን ፀጥታው ዋጠው"
"ወንድሞቼ የአባቶቻችን መልካም ሥራ የሚመለሰው ባህልና.ደንባቸውን በመጠበቅ ነው" ተዚህ ታፈነገጥን የሚያድነው እንሰሳ ላይ ማነጣጠር እንዳልቻለ አነር መሮጥ እንጂ የምንይዘው አይኖርም ሁሉም ያምረናል፤ አረንጓዴ ሁሉ ይበላል? ኮሽም: ዶቅማ ይሆናል?- የእኛ ህይወት የአባቶቻችንን ፈለግ በመከተል የሚመራ
ነው፤ እነሱ ያዩትን ዓለምና ደስታ ለማግኘት ከዱካቸው ዝንፍ ማለት የለብንም ተዚያ ታፈነገጥን ግን እሾህ አለ እንቅፋት አለ… ዳመና
ከሰማዩ ላይ ይጠፋል ከብትና ምድሯ ይነጥፋሉ በሽታ ይበዛል ከዚያ ያኔ ቀያችን አጥንት ሰላማችን ቆምጭሮ ሁከት
ይከመርበታል እፅዋት መብቀል ያቆማሉ፤ ባንኪሞሮ የአነደደው
እሳት ይጠፋና ጥንት እንደነበረው ቀያችንን ዳፍንት ይውጠዋል
ባዶ ይሆናል! እና ተልባችን እንምከር ወንድሞቼ!" ብለው እጃቸውን
አወራጭተው ጦሩን ስመው ዝም አሉ ሌሎች ሽማግሎችም እንዲሁ
የሚሰማቸውን ሲናገሩ ቆዩና ጥፋቶች በመጀመሪያው
ተናጋሪ ተዘረዘሩ።
በአካል ለዘለዓለም
ለተለዩን በርቲና ቃላ መደረግ የሚገባው ደንብ አልተሰራላቸውም "አሉ” እንዳንል የሉም የሉም
እንዳንል ደግሞ ደንቡን የምትጠብቀው ነፍሳቸው አንዴ በወፍ ሌላ ጊዜ በአሞራ ወይንም በንፋስ … መልክ እየመጣች ከእኛ ጋር ናት ንግግራቸውን ገተው የሽማግሎችን የመንደሯን የአካባቢውን ትንፋሽ አዳመጡና
ነጯ ሐመር ይዛው የመጣችብን ስም የለሽ: ጢስ ተፊ አውሬም እዚሁ ከእኛ ጋር እየኖረ ነው ሲበላ ባናየውም ሲጋት ግን
በዐይናችን በብረቱ አይተነዋል ከዚያ እንደ ጅብ አጉረምርሞ ዐይናችን እያዬ ግማቱን ለቆብን ይሄዳል "
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
የወሮ መንደር ሽማግሎች ከሁለቱ መንደሮች መሃል ካለችው ትንሽ ሜዳ ግማሽ ክብ ሰርተው በርኮታቸው ላይ ተቀምጠዋል" ባለ
ጴሮው፥ ሹልሹላው፥ የሰጎን ላባ ፀጉሩ ላይ የሰካው ሁሉም በተመስጦ ስብሰባው እስኪጀምር ለውይይቱ ህሊናቸውን ይሳስላሉ ህፃናት ከሽማግሎች ርቀው
እንቧይ እየተቀባበሉ
ይጫወታሉ ጋልታምቤ ከቤቱ ወደ ሜዳው በምትወስደው ቀጭን ጎዳና ሄዶ ከሽማግሎች ጋር ተቀላቀለ ሌሎችም ከያቅጣጫው እየመጡ
ተደባለቁ„
ረጅም ጦር የያዙት የመንደሩ አለቃ (ዘርሲ) ከተቀመጡበት
ተነሱና ከወገባቸው ከታጠቁት ዝናር ጩቤ አውጥተው ጎረምሶች
የያዙትን ለፍላፊ ፍየል በቁሙ ጉሮሮው ላይ ወጉትና ፍየሉ ሲወድቅ
ከደሙ ጦራቸው ላይ ከፈርሱ ደግሞ ባታቸውን ቀባ-ቀባ አድርገው
ሄድ መለስ: ሄድ መለስ ብለው ንግግር ጀመሩ
"ጥሩ ነው! ዝናቡ መጥቷል መሬቷ ሳር አብቅላለች፥
ተራሮች እንደ ልጃገረድ አጊጠዋል ድንጉላ ቢራቢሮዎች፥ ወፎች
ይበራሉ" ንቦች አበባቸውን እየቀሰሙ ወደ ቀፎቻችን ይተማሉ፥ ውሃ የጠማት ምድር እምትጠጣው አግኝታለች እኛም የምንጠጣውን ከስኬ ይሰጠናል አሸዋውን ስንጭረው ውሃ መሬቷን በጧር ስንወጋት ማሽላ እናገኛለን ዳመናውን ሰርስራ
በምትወጣው ጨረቃም ልጆቻችን ይደሰታሉ
እንግዲህ ተቀያችን: ከዚች
አባቶቻችን ካቆዩን ምድር ምን ጎደለ!" ብለው ዝም አሉ የሽማግሎች
አለቃ" እንደገና ሄድ መለስ እያሉ ሁሉንም በዐይናቸው እየቃኙ
ብዙዎቹ ተሰብሳቢዎች ዐይናቸው ያለው ሌላ ቦታ ነው ሐመር ላይ ነገር በዐይን አይገባም' ነገር የሚደመጠው በልቦና ነው፤
ልቦና ያያል ልቦና ይሰማል
ልቦና ይመራመራል ልቦና
ይወስናል" በልቦና ለማየትና ለመስማት ግን ፀጥታ ያስፈልጋል ውስጣዊ እርጋታ የሃሳብ ማዕበል የሌለበት መተራመስ የተረጋጋበት ሊሆን ይገባል" ሐመር ላይ ሽበት ብቻ
ለሽምግልና አያበቃም፤
ጀግንነት ብቻ አያስከብርም
ማህበራዊ ችግርን ለመፍታት በጥንቃቄ ውሉን ፈልጎ አግኝቶ ትብትቡን
የሚፈታ ህሊናው ቀልጣፋ ከጀግንነቱም ከፍርድ አዋቂነቱም ሁለገብ ችሎታ ያለው መሆን ያሻል ለሽምግልና ለመታጨት
"ጥሩ ነው! የአባቶቻችን መንፈስ ከእኛ ጋር አለ እንዳንራብ መከራ እንዳይበዛብን ዝንጉ እንዳንሆን የነሱ መንፈስ እንደ ዛፍ ጥላ ከለላ ይሆነናል ይሁን እንጂ በአባቶቻችን የነበረው ችግር አሁንም
አለ አሁንም የአባት ጠላት አለን አሁንም የአባት ጠላቶች እያዘናጉ የከብቶቻችንን ጅራት ሊጎትቱ የሚስቶቻችንን እጅ ሊስቡ፥ የላሞቻችንን ጡት ሊያልቡ ይፈልጋሉ ተናጋሪው ንግግራቸውን ገተው ዙሪያ ገቡን እያዩ ፀጥ አሉ የኦሞ ወንዝ ቆሞ ያውቃል? ውሃ ታግዶ ይቆማል? ያባት
ደንብም እንዲሁ ነው፤ ሁሌም ከልጅ ወደ ልጅ ግድቡ በሽማግሎች
እየተከፈተ ከላይ እየወረደ የመጣው ወደሚቀጥለው
ትውልድ እየቶንዶለዶለ
ይፈሳል" ለዚህ ነው ከስኬ ሲጫር ውሃ: የእኛ ልብ
ሲቆፈር ደግሞ ያባት ደንብና ባህል የሚፈልቀው፤ ከእኛ መሃል ልቡ ሲቆፈር የአባት ደንብና ባህል የማያፈልቅ ደረቅ ካለ ግን ከጠላት
የተወረወረብን ድንጋይ ስለሆነ አምዘግዝገን መወርወር፥ ካካባቢያችን
ማጥፋት ይኖርብናል" ተናጋሪው ሽማግሌ ንግግራቸውን ገትተው
የተናገሩትን እንደገና በህሊናቸው አጣጣሙት።
"ወንድሞቼ የአባቶቻችን መንፈስ ከእኛ ጋር ነው
የምንሰራውን እነሱ ካቆዩን ደንብ ጋር ካላመዛዘነው እንደ ዱር ጉንዳን ማን እንደቆመብን ሳይታወቅ፤ ምንነታችንም ሳይጠየቅ አውራ እንደሌለው የሚያስተባብረው እንዳጣ ንብ በየጢሻው እንበተናለን
እንጨት ቆርጠን ሳር አጭደን ለንብ ቀፎ እየሰራን: እኛ ግን ተሰርቶ የቆየንን የአባት ደንብ ደህንነቱን
በመጠበቅ ለልጅ ልጆቻችን ማስተላለፍን ዘንግተናል" ከጉንዳን: ከንብ አንሰን የአባት ደንብ እየሻርን ነው: ትብብራችን እየላላ ነው፥ ወኔያችን ተሸንቁሮ
ንፋስ እየገባው ነው." እንደገና ቃኙት ተሰብሳቢውን በዝምታ።
"አውሬ ይሁን ወፍ የማይታወቅ ጉድ በአራት እግሩ መንደራችን እየመጣ ሲቆም በሰፊው ሆዱ ሴቶቻችንን እየሸፋፈኑ
እያቀፈ ሲወስድና ሲመልስ
ሴት ልጅ ወንድ የዘራውን ማብቀል ሲሳናት እኛ አልተቃወምንም! ኧረ ተው! የተቀበልነውን የማናቀብል ጅብ አንሁን ጅብ የሚኖረውና የሚሞተውም ለሆዱ ነው የአባት ደንብ የለው ለልጄ ማለት አያውቅ አፍንጫው ጥንብ እንዳሸተተ: ሆዱ ለመብላት እንደተስገበገበ
ኖሮ ይሞታል ለልጄ ሳይል ደንብ ሳይኖረው ጥንብ እንደ አማተረ ይሞታል ለሆዱ! የተናጋሪውን ሃሳብ ከሚያዳምጡት መካከል አንዱ ሽማግሌ
የዘርሲዎች አለቃ በተናገሩ ቁጥር "ህም ህም… "አሉ በሐመር የስብሰባ ደንብ አንዱ ሲናገር ሌላው ህም ህም ካለ ልቀጥል ልናገር ማለት ስለሆነ የሽማግሎች አለቃ የንግግር እድሉንና
ተናጋሪው የሚይዘውን ጦር አቀበሉ ተረኛው ሽማግሌ ጦሩን በቀኛቸው ይዘው ከፍየሉ ፈርስ ባታቸውንና ግንባራቸው ቀባ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ሽማግሎችን: ህፃናትን: መንደሩን: ዙሪያ
ገቡን ቃኙት ጦሩ እጃቸውን ነዘረው ስሜታቸውን በሙቀቱ አጋጋለው፤ ወኔያቸውን እንደ ብረቱ ጫፍ አጠነከረው የአያት
የአባቶቻቸው መንፈስ ከጦሩ ተነስቶ ወደ ልቦናቸው ተስለከለከ
ጥሩ ነው! የቀጋ ፍሬ ከሾላ ዛፍ የለቀመ ማነው ሾላና
ቀጋን ደባልቆ የሚበላ ግን አስተዋይ ነው ይህ ሰው የተፈጠረው ደግሞ እዚሁ እኛ ዘንድ ቡስካ ተራራ ላይ ነው ያ ሰው እሳት
አንድዶ የሚፈልጋቸውን መልካም መልካም ሰዎች በእሳት ብርሃን
ከያካባቢው ጠራቸው
እንግዲህ አያቶቻችን የባንኪሞሮን እሳት
እያዩ ከያቅጣጫው የተሰባሰቡ ናቸው እኒያን ፍሬዎች ቀጋና ሾላዎች ባንኪሞሮ ደባልቆ በሐመር ምድር በተናቸው"
አያቶቻችንና አባቶቻችን በቀሉ ከእኒያ ብሩክ ፍሬዎች ደግሞ እኛ በቅለን እህ! በተራችን እንድናፈራ ላደረጉን አባቶቻችን ውለታችን ምንድነው?" ብለው ዝም አሉ ሽማግሌው በጠየቁት ጥያቄ አንጀታቸው እየተላወሰ መልሱን ግን ፀጥታው ዋጠው"
"ወንድሞቼ የአባቶቻችን መልካም ሥራ የሚመለሰው ባህልና.ደንባቸውን በመጠበቅ ነው" ተዚህ ታፈነገጥን የሚያድነው እንሰሳ ላይ ማነጣጠር እንዳልቻለ አነር መሮጥ እንጂ የምንይዘው አይኖርም ሁሉም ያምረናል፤ አረንጓዴ ሁሉ ይበላል? ኮሽም: ዶቅማ ይሆናል?- የእኛ ህይወት የአባቶቻችንን ፈለግ በመከተል የሚመራ
ነው፤ እነሱ ያዩትን ዓለምና ደስታ ለማግኘት ከዱካቸው ዝንፍ ማለት የለብንም ተዚያ ታፈነገጥን ግን እሾህ አለ እንቅፋት አለ… ዳመና
ከሰማዩ ላይ ይጠፋል ከብትና ምድሯ ይነጥፋሉ በሽታ ይበዛል ከዚያ ያኔ ቀያችን አጥንት ሰላማችን ቆምጭሮ ሁከት
ይከመርበታል እፅዋት መብቀል ያቆማሉ፤ ባንኪሞሮ የአነደደው
እሳት ይጠፋና ጥንት እንደነበረው ቀያችንን ዳፍንት ይውጠዋል
ባዶ ይሆናል! እና ተልባችን እንምከር ወንድሞቼ!" ብለው እጃቸውን
አወራጭተው ጦሩን ስመው ዝም አሉ ሌሎች ሽማግሎችም እንዲሁ
የሚሰማቸውን ሲናገሩ ቆዩና ጥፋቶች በመጀመሪያው
ተናጋሪ ተዘረዘሩ።
በአካል ለዘለዓለም
ለተለዩን በርቲና ቃላ መደረግ የሚገባው ደንብ አልተሰራላቸውም "አሉ” እንዳንል የሉም የሉም
እንዳንል ደግሞ ደንቡን የምትጠብቀው ነፍሳቸው አንዴ በወፍ ሌላ ጊዜ በአሞራ ወይንም በንፋስ … መልክ እየመጣች ከእኛ ጋር ናት ንግግራቸውን ገተው የሽማግሎችን የመንደሯን የአካባቢውን ትንፋሽ አዳመጡና
ነጯ ሐመር ይዛው የመጣችብን ስም የለሽ: ጢስ ተፊ አውሬም እዚሁ ከእኛ ጋር እየኖረ ነው ሲበላ ባናየውም ሲጋት ግን
በዐይናችን በብረቱ አይተነዋል ከዚያ እንደ ጅብ አጉረምርሞ ዐይናችን እያዬ ግማቱን ለቆብን ይሄዳል "
👍18
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
ካርለት መሳተፍ የማትችለውን የሽማግሎች ስብሰባ በርቀት
እየተመለከተች አልፎ አልፎም የካሜራ ችፕስ በተደረገበት ባለዙም ካሜራዋ ፎቶ ስታነሳ ቆይታ ጎይቲን ፍለጋ ወደ መንደር
ተመለሰች
"ካርለት ነጋያ ... ነጋያ ... ያ ፈያው" አሉ ህፃናት የካርለትን ነጭ እጅ ለመያዝ እየተሽቀዳደሙ "ነጋያኒ ጎይቲ ዳ! ደህና ነኝ
ጎይቲ አለች ብላ ጠየቀቻቸው በሐመርኛ
"እእ ዳኒ" አለች አንዷ ህፃን ራሷን ዝቅ አድርጋ ሽቅብ
በመናጥ አለች ለማለት ካርለት መዝጊያ ወደሌለው መግቢያ ጎንበስ ብላ በጠባቧ በር ወደ ውስጥ ስታይ ምርግ በሌለው የእንጨት መከታ መሐል ለመሐል በሚገባው ብርሃን ጎይቲ በርከክ ብላ እጆችደ
ከወፍጮው መጅ ላይ ሳይነሱ ራሷን ብቻ ወደ በሩ መልሳ አየቻትደ ካርለት የጎይቲን ማራኪ ፈገግታና የምትወደውን ጥርሷን ስታይ የደስታ ስሜት ውርር አድርጓት እሷም ሳቀች ተሳሳቁ"
"አርዳ?" አለች ጎይቲ በአንገቷ እንደምትስባት ሁሉ አገጯን ወደ ታች እየሰበቀች ካርለት ፈገግ እንዳለች እሷን፥ ከኋላዋ
የተንጠለጠሉትን የቁርበት ልብሶች ግርግሙ ላይ የተንጠለጠሉትን
ዶላዎች (የወተት መያዣዎች) ግልጥጥ ያለውን የምድጃ ፍም:
በቀበቶው ጉጥ ላይ ቁልቁል የተንጠለጠለውን ክላሽንኮቭ ጠመንጃ
ልጆች አመዱን በውሃ በጥብጠው መግቢያው ጥግ ባለው የግድግዳ
ልጥፍ ላይ ያዩትን ለመሳል ያደረጉትን ጥረት ... በዐይኗ ስትቃኝ.
"አርዳ!" አለች ጎይቲ ደግማ አትገቢም! ለማለት ቃሉን ረገጥ አድርጋ።
"ፈያኔ" ብላ ካርለት እንደ ጅራት ከኋላዋ የተንጠለጠለውን
የፍዬል ቆዳዋን በግራ እጅዋ ወደ እግሮችዋ መሐል አስገብታ ቀኝ
እግሯን በማስቀደም በጠባቧ በር ሹልክ ብላ ገባች የሐመር ቤት
መዝጊያ የለውም ቀንም ሆነ ማታ እንግዳ የአባት ሙት መንፈስ ከመጣ ሁሌም ሳይጠብቅ: ደጅ ሳይጠና ሰተት ብሎ መግባት አለበት ትንሽዋ በር ደፍዋ ከፍ ያለ በመሆኑ ለከብትም ሆነ ለአውሬ
ለመግባት አታመችም ቤት ለሐመሮች መቀመጫና መተኛ እንጂ መቆሚያ አይደለም" ሁሉም ነገር ትርጉም ሊኖረው ይገባል
ስለሆነም ካለ ህፃናት በስተቀር በጣም አጭር ሰው እንኳ ጎንበስ ብሎ
ካልሆነ መቆም አይችልም ይህ የሆነው ደግሞ እንጨት ጠፍቶ ቦታ
ጠቦ ሳይሆን ለትርጉሙ ነው"
"ጎይቲ?"
"ዬ!"
ምነው ዛሬስ ስትፈጭ መዝፈን: ማንጎራጎሩን ተውሽው?" ብላ ጠይቃት ካርለት ፈገግ ብላ ጎይቲን ሳመቻት እንደ
ሐመር ሴቶች የልብ ሰላምታ ጎይቲ ካርለት ለጠየቀቻት መልስ ሳትሰጥ አንገቷን ደፍታ እጅዋ ወፍጮው
መጅ ላይ እንዳለ በተመስጦ ስታስብ ቆይታ በቀኝ እጅዋ ማሽላውን ግራና ቀኝ ሰብስባ ወደ ወፍጮው ጥርስ አስገብታ
ወገቧን ወደ ኋላና ወደ ፊት
እያረገረገች "ሸርደም: ሸርደም አድርጋ ፈጨችውና ብርኩማዋ ላይ ተቀመጠች
ከዚያ እኒያን ሐጫ በረዶ የመሳሰሉ ጥርሶችዋን
ገልጣ ለዓመል ያህል ፈርጠም አለችና
"ይእ!ካርለቴ ኧረ አሁን ሳንጎራጉር ነበር መቼ
እንጉርጉሮዬን እንደ አቆምኩት ግን እንጃ! አዝኜ እንኳን ቢሆን ሁልጊዜ መፍጨት ስጀምር እህሉ ከታች ሲደቅ እኔ ከላይ ትዝታዬን እየጨመርሁ እንጉርጉሮዬን አቀልጠው ነበር አሁን እኮ ኮቶ እግሯ
ወጣ ከማለቱ ነው አንች የመጣሽ ከኮቶ ጋር እየተከራከርን ሁላ እዘፍን ነበር በኋላ ግን ኮቶ ለመሄድ ስትቁነጠነጥ እያወራች እንድትቆይ ብዙ
ክርክር ገጠምኋት
ታውቂያታለሽ ተከራክራ ተከራክራ ካልረታች እንደ ፍየል ልዋጋ ስትል ታስቀኛለች ስለዚህ ጥላኝ ከምትሄድ ብዬ ነገር ጀመርኋት
"ኮቶ ከተማ አትሄጅም?" ስላት
"ይእ! ኧረ ምን አልሁሽ እቴ እኔስ ያገሬ ጅብ ይብላኝ
አለችኝ ትንሽ ላስለፍልፋት ብዬ እኔ ግን መበላቴ ታልቀረ የጅብ ዘመድ አልመርጥም አልኋት አይምሰልሽ ጅሊት! ያገርሽ ጅብ ገሎ ነው የሚበላሽ የሰው አገር ጅብ ግን እየበላ ነው የሚገልሽ ስትለኝ ይእ! አንች ምነው ታልጠፋ አውሬ ጅብን እንዲህ ዘመድ
አዋቂ አደረግሽው?
አልኳት‥ ይሄ እንኳ ምሳሌ ነው ስትለኝ ሞጥሟጤ ምሳሌሽን ቀይሪያ!ታለበለዚያ ካለ
ጥንባቸው ሌላ
የማያውቁትን ጅቦች ካለስማቸው
ስም ሰጥተሽ ቅዱስ አድርገሽ ታውሬው ሁሉ አታቀያይሚያቸው" ብላት ወገቤን ደቅታኝ ሹልክ ብላ ሄደች ከዚያ ማንጎራጎር ጀምሬ ነበር ወዲያው ግን ድምፄ ለከት የለሽ ሆኖ ልቤ ግንድ የሚያመሽክ ምስጥ ይርመሰመስበት ጀመር
"ምን ሆነሽ ነው ጎይቲ የምን ጭንቀት ነው?"
"ወደው አይስቁ አለ ያገሬ ሰው ..." ብላ ጎይቲ ከትከት ብላ ስቃ።
"ይእ! ምነው እንዳንች ጅል ሆኜ እድሜ ልኬን ስጠይቅ
በኖርሁ" ስትላት ተያይዘው እንደገና ተሳሳቁ
"ካርለቴ! እውን ሴት ልጅ እግርና እጅዋ የሚያጥረው፥
ቀትረ ቀላል ሆና ድምጿ የሚሰለው ... ለምን እንደሆን አታውቂም?
"አላውቅም ጎይቲ ለምንድን ነው?"
"ይእ! እንግዲያ ዝናብ እንደበዛበት ማሽላ ታለ ፍሬ መለል ብለሽ ያደግሽ አገዳ ነሻ! ሙች አንችስ ተህፃን አትሻይም አንቺ እኮ! ተንግዲህ ወዲያ ትልቅ ሰው ነሽ! ጉያሽና ልብሽ ላይ የትዝታ ምሰሶ የተተከለ
ፈጭተሽ የምታበይ ጭሮሽ ውሃ ቀድተሽ ለጥም
መቁረጫ የምታጠጭ
የወንድ ልብ ሲጎመራ ጫካ መሃል ገብተሽ የምትካፈይ
ፍቅርሽን እንደ ህፃን ልጅሽ የምትግች ትልቅ ሴት እኮ ነሽ?" ትልቅ ሴት እኮ ነሽ?"
"ጎይቲ የባሰ ግራ ገባኝ?"
"ይእ! እንዲያ ይሻላል! ቁም ነገር አታውቂም ብዬ ተመንገር ሌላ እህ ላሳይሽ?" ብላ ጎይቲ በአድናቆት ጨብጨብ ጨብጨብ አድርጋ በሣቅ ተፍለቀለቀች
ካርለት ከተቀመጠችበት
ፈገግ ብላ ተነስታ ጎይቲን ገፋ አድርጋት የወፍጮውን መጅ በግራ እጅዋ ይዛ ከሾርቃው በቀኝ
እጅዋ ማሽላውን አፍሳ ጨምራ
"እሽ እኔ እፈጫለሁ አንች ንገሪኝ?" አለቻት
"ይእ! እውነት ታላወቅሽውማ እነግርሻለሁ እንጂ ብላ እግሯን ዘርግታ ቁርበቱ ላይ ቁጭ አለች ጎይቲ ወደ ቁምነገር
ስትመለስ የሚያስጨንቃትን
ለመናገር ስትዘጋጅ ውስጧን የሚጎማምደው ችግሯ የፈገግታ ፀዳሏን እየቸለሰ አከሰመው ደሟ
እንደቀትር ማዕበል ደረቱን ገልብጦ እየዘለለ በመፍረጥ አረፋ ደፈቀ
ታወከ
"ሐመር ላይ ሴት ልጅ የግል ችግር የለባትም እምትበላውን መሬቷ እምትጠጣውን ላሞች: ፍቅርን ደግሞ የሐመር ወንዶች እንደ ማሽላ ገንፎ እያድበለበሉ ያውጧታል ሴት ልጅ ወንዝ
ብትሄድ እንጨት ለቀማ ጫካ ብትገባ እህል ልታቀና ገበያ ብትወጣ ብቻዋን አትሆንም ሰው ከብቶች: ዛፎች አሉላት ሴት ብቻዋን ችግር የሚገጥማት የማትወልድ ስትሆን ነው መሐንነት ትታይሻለች ያች ፀሐይ " ዝቅ ብላ በግርግዳው ቀዳዳ ጮራዋን ፈንጥቃ የምትንቦገቦገውን የረፋድ ፀሐይ እያሳየቻት
"ይኸውልሽ መሐንነት ያችን በሙቀት የምትነድ እሳት ዘላለም እንደ ጨቅላ ህፃን ደረትሽ ላይ ታቅፈሽ መኖር: ታቅፈሽ መሞት ነው" ተዚያ እድሜ ልክሽን መቃጠል: መንደድ ነው"
"መሐንነቱ የመጣብሽ ሳታስቢው የሴት ብልትሽን ውሃ ነክቶት ይሆናል ሆን ብለሽ ባታደርጊውም ትዕዛዝ ነውና ቅጣቱ ቃጠሎው ወደ ገለብ ብትሮጭም አታመልጭውም ስትቃጠይ ደግሞ ሰው የሻጉራ እያዬ ይሸሽሻል ባይሆን ከቃጠሎሽ ባይጠቅምሽም
ለእነሱም ባይጠቅማቸውም ለአባትሽ ለእናትሽ ለእህትሽ
ለዘመዶችሽ ታካፍያቸዋለሽ የተረገመ ቤተሰብ እያሰኘሽ" ብላ ዝም አለች ጎይቲ እንደተላጠ ጣውላ ሰውነቷ ሟሾ
ግዙፍነት ለካ በአጥንትና ስጋ ብቻ አይደለምና መጠንም በህሊና ይወሰናል ውበትና ቁመና ህሊና በሚፈጥረው መተማመን ተገዥ ነውና! እያለች ካርለት ጎይቲን እያየች ስታስብ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ሦስት
ካርለት መሳተፍ የማትችለውን የሽማግሎች ስብሰባ በርቀት
እየተመለከተች አልፎ አልፎም የካሜራ ችፕስ በተደረገበት ባለዙም ካሜራዋ ፎቶ ስታነሳ ቆይታ ጎይቲን ፍለጋ ወደ መንደር
ተመለሰች
"ካርለት ነጋያ ... ነጋያ ... ያ ፈያው" አሉ ህፃናት የካርለትን ነጭ እጅ ለመያዝ እየተሽቀዳደሙ "ነጋያኒ ጎይቲ ዳ! ደህና ነኝ
ጎይቲ አለች ብላ ጠየቀቻቸው በሐመርኛ
"እእ ዳኒ" አለች አንዷ ህፃን ራሷን ዝቅ አድርጋ ሽቅብ
በመናጥ አለች ለማለት ካርለት መዝጊያ ወደሌለው መግቢያ ጎንበስ ብላ በጠባቧ በር ወደ ውስጥ ስታይ ምርግ በሌለው የእንጨት መከታ መሐል ለመሐል በሚገባው ብርሃን ጎይቲ በርከክ ብላ እጆችደ
ከወፍጮው መጅ ላይ ሳይነሱ ራሷን ብቻ ወደ በሩ መልሳ አየቻትደ ካርለት የጎይቲን ማራኪ ፈገግታና የምትወደውን ጥርሷን ስታይ የደስታ ስሜት ውርር አድርጓት እሷም ሳቀች ተሳሳቁ"
"አርዳ?" አለች ጎይቲ በአንገቷ እንደምትስባት ሁሉ አገጯን ወደ ታች እየሰበቀች ካርለት ፈገግ እንዳለች እሷን፥ ከኋላዋ
የተንጠለጠሉትን የቁርበት ልብሶች ግርግሙ ላይ የተንጠለጠሉትን
ዶላዎች (የወተት መያዣዎች) ግልጥጥ ያለውን የምድጃ ፍም:
በቀበቶው ጉጥ ላይ ቁልቁል የተንጠለጠለውን ክላሽንኮቭ ጠመንጃ
ልጆች አመዱን በውሃ በጥብጠው መግቢያው ጥግ ባለው የግድግዳ
ልጥፍ ላይ ያዩትን ለመሳል ያደረጉትን ጥረት ... በዐይኗ ስትቃኝ.
"አርዳ!" አለች ጎይቲ ደግማ አትገቢም! ለማለት ቃሉን ረገጥ አድርጋ።
"ፈያኔ" ብላ ካርለት እንደ ጅራት ከኋላዋ የተንጠለጠለውን
የፍዬል ቆዳዋን በግራ እጅዋ ወደ እግሮችዋ መሐል አስገብታ ቀኝ
እግሯን በማስቀደም በጠባቧ በር ሹልክ ብላ ገባች የሐመር ቤት
መዝጊያ የለውም ቀንም ሆነ ማታ እንግዳ የአባት ሙት መንፈስ ከመጣ ሁሌም ሳይጠብቅ: ደጅ ሳይጠና ሰተት ብሎ መግባት አለበት ትንሽዋ በር ደፍዋ ከፍ ያለ በመሆኑ ለከብትም ሆነ ለአውሬ
ለመግባት አታመችም ቤት ለሐመሮች መቀመጫና መተኛ እንጂ መቆሚያ አይደለም" ሁሉም ነገር ትርጉም ሊኖረው ይገባል
ስለሆነም ካለ ህፃናት በስተቀር በጣም አጭር ሰው እንኳ ጎንበስ ብሎ
ካልሆነ መቆም አይችልም ይህ የሆነው ደግሞ እንጨት ጠፍቶ ቦታ
ጠቦ ሳይሆን ለትርጉሙ ነው"
"ጎይቲ?"
"ዬ!"
ምነው ዛሬስ ስትፈጭ መዝፈን: ማንጎራጎሩን ተውሽው?" ብላ ጠይቃት ካርለት ፈገግ ብላ ጎይቲን ሳመቻት እንደ
ሐመር ሴቶች የልብ ሰላምታ ጎይቲ ካርለት ለጠየቀቻት መልስ ሳትሰጥ አንገቷን ደፍታ እጅዋ ወፍጮው
መጅ ላይ እንዳለ በተመስጦ ስታስብ ቆይታ በቀኝ እጅዋ ማሽላውን ግራና ቀኝ ሰብስባ ወደ ወፍጮው ጥርስ አስገብታ
ወገቧን ወደ ኋላና ወደ ፊት
እያረገረገች "ሸርደም: ሸርደም አድርጋ ፈጨችውና ብርኩማዋ ላይ ተቀመጠች
ከዚያ እኒያን ሐጫ በረዶ የመሳሰሉ ጥርሶችዋን
ገልጣ ለዓመል ያህል ፈርጠም አለችና
"ይእ!ካርለቴ ኧረ አሁን ሳንጎራጉር ነበር መቼ
እንጉርጉሮዬን እንደ አቆምኩት ግን እንጃ! አዝኜ እንኳን ቢሆን ሁልጊዜ መፍጨት ስጀምር እህሉ ከታች ሲደቅ እኔ ከላይ ትዝታዬን እየጨመርሁ እንጉርጉሮዬን አቀልጠው ነበር አሁን እኮ ኮቶ እግሯ
ወጣ ከማለቱ ነው አንች የመጣሽ ከኮቶ ጋር እየተከራከርን ሁላ እዘፍን ነበር በኋላ ግን ኮቶ ለመሄድ ስትቁነጠነጥ እያወራች እንድትቆይ ብዙ
ክርክር ገጠምኋት
ታውቂያታለሽ ተከራክራ ተከራክራ ካልረታች እንደ ፍየል ልዋጋ ስትል ታስቀኛለች ስለዚህ ጥላኝ ከምትሄድ ብዬ ነገር ጀመርኋት
"ኮቶ ከተማ አትሄጅም?" ስላት
"ይእ! ኧረ ምን አልሁሽ እቴ እኔስ ያገሬ ጅብ ይብላኝ
አለችኝ ትንሽ ላስለፍልፋት ብዬ እኔ ግን መበላቴ ታልቀረ የጅብ ዘመድ አልመርጥም አልኋት አይምሰልሽ ጅሊት! ያገርሽ ጅብ ገሎ ነው የሚበላሽ የሰው አገር ጅብ ግን እየበላ ነው የሚገልሽ ስትለኝ ይእ! አንች ምነው ታልጠፋ አውሬ ጅብን እንዲህ ዘመድ
አዋቂ አደረግሽው?
አልኳት‥ ይሄ እንኳ ምሳሌ ነው ስትለኝ ሞጥሟጤ ምሳሌሽን ቀይሪያ!ታለበለዚያ ካለ
ጥንባቸው ሌላ
የማያውቁትን ጅቦች ካለስማቸው
ስም ሰጥተሽ ቅዱስ አድርገሽ ታውሬው ሁሉ አታቀያይሚያቸው" ብላት ወገቤን ደቅታኝ ሹልክ ብላ ሄደች ከዚያ ማንጎራጎር ጀምሬ ነበር ወዲያው ግን ድምፄ ለከት የለሽ ሆኖ ልቤ ግንድ የሚያመሽክ ምስጥ ይርመሰመስበት ጀመር
"ምን ሆነሽ ነው ጎይቲ የምን ጭንቀት ነው?"
"ወደው አይስቁ አለ ያገሬ ሰው ..." ብላ ጎይቲ ከትከት ብላ ስቃ።
"ይእ! ምነው እንዳንች ጅል ሆኜ እድሜ ልኬን ስጠይቅ
በኖርሁ" ስትላት ተያይዘው እንደገና ተሳሳቁ
"ካርለቴ! እውን ሴት ልጅ እግርና እጅዋ የሚያጥረው፥
ቀትረ ቀላል ሆና ድምጿ የሚሰለው ... ለምን እንደሆን አታውቂም?
"አላውቅም ጎይቲ ለምንድን ነው?"
"ይእ! እንግዲያ ዝናብ እንደበዛበት ማሽላ ታለ ፍሬ መለል ብለሽ ያደግሽ አገዳ ነሻ! ሙች አንችስ ተህፃን አትሻይም አንቺ እኮ! ተንግዲህ ወዲያ ትልቅ ሰው ነሽ! ጉያሽና ልብሽ ላይ የትዝታ ምሰሶ የተተከለ
ፈጭተሽ የምታበይ ጭሮሽ ውሃ ቀድተሽ ለጥም
መቁረጫ የምታጠጭ
የወንድ ልብ ሲጎመራ ጫካ መሃል ገብተሽ የምትካፈይ
ፍቅርሽን እንደ ህፃን ልጅሽ የምትግች ትልቅ ሴት እኮ ነሽ?" ትልቅ ሴት እኮ ነሽ?"
"ጎይቲ የባሰ ግራ ገባኝ?"
"ይእ! እንዲያ ይሻላል! ቁም ነገር አታውቂም ብዬ ተመንገር ሌላ እህ ላሳይሽ?" ብላ ጎይቲ በአድናቆት ጨብጨብ ጨብጨብ አድርጋ በሣቅ ተፍለቀለቀች
ካርለት ከተቀመጠችበት
ፈገግ ብላ ተነስታ ጎይቲን ገፋ አድርጋት የወፍጮውን መጅ በግራ እጅዋ ይዛ ከሾርቃው በቀኝ
እጅዋ ማሽላውን አፍሳ ጨምራ
"እሽ እኔ እፈጫለሁ አንች ንገሪኝ?" አለቻት
"ይእ! እውነት ታላወቅሽውማ እነግርሻለሁ እንጂ ብላ እግሯን ዘርግታ ቁርበቱ ላይ ቁጭ አለች ጎይቲ ወደ ቁምነገር
ስትመለስ የሚያስጨንቃትን
ለመናገር ስትዘጋጅ ውስጧን የሚጎማምደው ችግሯ የፈገግታ ፀዳሏን እየቸለሰ አከሰመው ደሟ
እንደቀትር ማዕበል ደረቱን ገልብጦ እየዘለለ በመፍረጥ አረፋ ደፈቀ
ታወከ
"ሐመር ላይ ሴት ልጅ የግል ችግር የለባትም እምትበላውን መሬቷ እምትጠጣውን ላሞች: ፍቅርን ደግሞ የሐመር ወንዶች እንደ ማሽላ ገንፎ እያድበለበሉ ያውጧታል ሴት ልጅ ወንዝ
ብትሄድ እንጨት ለቀማ ጫካ ብትገባ እህል ልታቀና ገበያ ብትወጣ ብቻዋን አትሆንም ሰው ከብቶች: ዛፎች አሉላት ሴት ብቻዋን ችግር የሚገጥማት የማትወልድ ስትሆን ነው መሐንነት ትታይሻለች ያች ፀሐይ " ዝቅ ብላ በግርግዳው ቀዳዳ ጮራዋን ፈንጥቃ የምትንቦገቦገውን የረፋድ ፀሐይ እያሳየቻት
"ይኸውልሽ መሐንነት ያችን በሙቀት የምትነድ እሳት ዘላለም እንደ ጨቅላ ህፃን ደረትሽ ላይ ታቅፈሽ መኖር: ታቅፈሽ መሞት ነው" ተዚያ እድሜ ልክሽን መቃጠል: መንደድ ነው"
"መሐንነቱ የመጣብሽ ሳታስቢው የሴት ብልትሽን ውሃ ነክቶት ይሆናል ሆን ብለሽ ባታደርጊውም ትዕዛዝ ነውና ቅጣቱ ቃጠሎው ወደ ገለብ ብትሮጭም አታመልጭውም ስትቃጠይ ደግሞ ሰው የሻጉራ እያዬ ይሸሽሻል ባይሆን ከቃጠሎሽ ባይጠቅምሽም
ለእነሱም ባይጠቅማቸውም ለአባትሽ ለእናትሽ ለእህትሽ
ለዘመዶችሽ ታካፍያቸዋለሽ የተረገመ ቤተሰብ እያሰኘሽ" ብላ ዝም አለች ጎይቲ እንደተላጠ ጣውላ ሰውነቷ ሟሾ
ግዙፍነት ለካ በአጥንትና ስጋ ብቻ አይደለምና መጠንም በህሊና ይወሰናል ውበትና ቁመና ህሊና በሚፈጥረው መተማመን ተገዥ ነውና! እያለች ካርለት ጎይቲን እያየች ስታስብ
👍19👎1
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አራት
ዘርሲዎች ግማሽ ክብ ሰርተው ከመንደሩ ራቅ ብላ ዙሪያ ገቡን ከምታሳየው
የግራር ዛፍ ስርቁጭ ብለዋል ጩሉሌዎች
አንገታቸውን ቁልቁል ደፋ አድርገው በዛ ዙሪያ ያንዣብባሉ: ነፋሱ
ቅጠሎችን ጎንበስ ቀና እያደረገ ይነፍሳል
ከፊት ለፊታቸው ርጥብ
ቅጠል ተነጥፏል መሃል ላይ ጎረምሶች የተጠበሰውን የፍየል ስጋ እየቆራረጡ የፍሪንባውን ሥጋ በእድሜ ለገፉትና በጀግንነታደው ለሚታወቁት ለሌሎች ደግሞ ከተለያየውደ የስጋ አይነት እፊት ለፊታቸው ካለው ቅጠል አስቀመጡ" ህፃናት ጨዋታቸውን አቁመው ራቅ ብለው ሲቁለጨለጩ ቆይተው እደላው አልቆ መብሉ ሲጀመር ወደየአባቶቻቸው ጉያ ተሸጉጠው ዳረጎታቸውን እየተቀበሉ ከአጥንት ጋር መታገል ጀመሩ በመጨረሻ የሚበላው ከተበላ: ቀሪውን ደግሞ ጎረምሶቹ ካቀለጣጠፉት በኋላ ወጣቶቹ ቅጠሉን ሰብስበው ጥለው
ከስብሰባው አካባቢ ርቀው ሄዱ።
የሽማግሎች አለቃ ጦራቸውን ይዘው ከተቀመጡበት ተነስተው
ከፈርሱ እግራቸውን ቀባ አድርገው ወዲህ ወዲያ ወዲያ ወዲህ አሉና፣
"የአባት ደንብ ጥሩ ነው" በልክ መብላት የአባቶቻችን ባህል ነው አባቶቻችን የራበውና የጠገበ ትክክል ፍርድ አይሰጥም ይሉ
ነበር" የጠገበ ወንድ ሴት ማለት ነው መሳቅ ቧልት ይወዳል ከብቶችን አይፈቅድም ጫካውን አይቃኝም ከጓደኞቹ ጋር
አይመክርም መዝለል አይችልም መቀመጥና ማንጎላጀት ይወዳል
ትክክለኛ ፍርድ በዚህ ምክንያት አይሰጥም ይሉ ነበር አባቶቻችን" ሽማግሌው እቱፍ: እቱፍ
ብለው የጦሩን ዘንግ በምራቃቸው ቀባ ቀባ እያደረጉ ሽማግሎችን:
የአባታቸውን አገር አድማስ እየተዟዟሩ አይተው
አባቶቼ የራበውም ከጠገበ አይሻልም ይሉ ነበር የራበው ሰው ሰነፍ ነው
ሲኖረው አያውቅበትም
የወደቀችው ጀንበር:
የጠፋችው ጨረቃ ተመልሰው የሚመጡ
አይመስሉትም እንደ
አጋሰስ ፈረስ ዘመዶቹ ለመቋቋሚያ የሰጡትን ፍየሉንም፥ በጉንም
ከብቱንም: እህሉንም ብቻውን እየበላ ነገን ዘንግቶ: ልጆቼ: የአባቴ
ምክር ሳይል ሁሉን ያሟጥጥና የሚያልበው ሲያጣ የሚበላው
ሲቸግረው ሰውን: መሬቷን: ቦርጆን: አባቶቹን ይራገማል" ሆዱን
ለመሙላት ይቀማል ይዋሻል … ፍቅር አያውቅም ዘመድ ወገን አይለይም
አያስተውልም፤ ጨካኝ ነው
በዚህ ምክንያት
አባቶቻችን የራበው ሰው ትክክል አይፈርድም ይሉ ነበር አባቶቻችን ትክክል ናቸው ወንድሞቼ ጥጋብ ልቦናን ያዛባል ረሃብ ደግሞ ተስፋ መቁረጥንና ጥላቻን ያመጣል ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ ሁለቱም ያስዋሻሉ" ብለው በርኮታቸው ላይ ቁጭ አሉ
ዝምታው ቀጠለ ሐመር ላይ ተረትን ሽማግሌ ለሌላው ማስታወስ እንጂ አይጨርሰውም የሰሙት እኩል: የፈፀሙት እኩል … ስለሆነ ተረት ጨራሽ አዳማጭ የለውም"
"በሉ ተናገሩ?" አሉ ሽማግሌው ከጥቂት ቆይታ በኋላ ጥሩ ነው! ከወደ መሃል አንዱ ድምፅ አሰሙ ገልመጥ ብሎ ያዬ የለም ሁሉም ግን አባባላቸውን በጆሮው ቀልቧል።
"ጥሩ ነው!- በአካል ተለይተውን ነፍሶቻቸው ደንቡን ጥበቃ አብረውን ላሉት ወንድሞቻችን ተገቢው ደንብ የሚሰራበት
ቀን ይመረጥ ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው በየበረሃው የአሉትን ተባት በግና ፍየሎች ከብቶችን ያስመጡ" በየመንደሩ ለሚኖሩት ዘመድ ጓደኞችም ጥሪ ይላክ ለዚያ ደሞ ዛሬ ቀኑ ተቆርጦ ቋጠሮ ይዘጋጅ አሉ።
የሽማግሎች አለቃ ሌላ ኃሳብ አለመኖሩን በዝምታደ ጠበቁና አንድ ጎረምሳ ጠርተው ልጥ አምጣ አንተ" አሉት ልጡ መጣ
"ስንት ላይ ይቋጠር?"
"መከን ተቢ" አሉ አንድ ሽማግሌ በስተግራ በኩል
ከተቀመጡት ሰላሳ ለማለት ልጡ ሰላሳ ላይ ተቋጥሮ ለሟቹ ታናሽ ወንድም
ተሰጠው" የሽማግሎች አለቃ አንዱን ችግር
በመቋጨታቸው
"ባይሮ ኢሜ" አሉ ሽማግሎችን እግዜር
ይስጣችሁ ለማለት
"በሉ ቀጥሉ?" አሉ የስብሰባው መሪ
"ጥሩ ነው!" አለ ልጅ እግሩና የአባቱን ጠላት ገሎ በቅርቡ
ከሽማግሌዎች ጋር ለመቀመጥ እድል ያገኘው ሰለምቤ፤ "ጥሩ ነው!
ታለውሻ በቀር አባቶቻችን ከአውሬ ጋር አልኖሩም እና ካርለቴ ይዛብን የመጣችውን አውሬ በጥይት አጉኖ ራቅ አድርጎ መቅበር ነው "አለ ገና የጎረምሳነት ባህሪው ሙሉ በሙሉ ያልቀዘቀዘለት ወጣቱ ሽማግሌ አለመብሰሉ በአነጋገሩ ፍጥጥ ብሎ እየታየበት።
"ጥሩ ነው! አውሬ ማለት ከብት የሚበላ ችግር የሚፈጥር ነው የነጯ ሐመር የካርለቴ አራት እግር አውሬ ሳይሆን መሂና
ነው የሚባል አባቶቻችን ደሞ መሂና የሚባል አውሬ አለ አላሉንም ደሞስ የካርለቴ መሂና እንደ ፈረስ እየጫነን ገበያ እያመላለሰን ነው እና መኖሩ ምን ጎዳ! አሉ ግራሯን የተደገፉት አንድ ዐይና
የአባት ደንብ እየሻርን ያ ይጎዳል ይሄ ይጠቅማል
ካልንማ ይህች አገርና ይህ ህዝብ መዓት ይመጣበታል" በነሱ ጊዜ ያልነበረ አውሬ አሁንም መኖር የለበትም " አሉ አገጫቸውን በግራ
እጃቸው ደግፈው የቆዩት ሽማግሌ ከዚያ ክርክሩ ከተለያዬ አቅጣጫ
መቅረቡ ቀጠለ
በአባቶቻችን ደንብ ፍየል ቢመጣ ፍየል ጋጥ: ከብት
ቢመጣ ከብቶች በረት ሰው ቢመጣ ወደ ሰዎች መኖሪያ ጎጆ ይገባል እህ እንዲህ እስተሆነ ድረስ የካርለቴ መሂና የሚገባ
ፍየሎች ጋጥ ነው? ከከብቶች በረት ነው? ወይንስ ከሰዎች ጋር ጎጆ
ውስጥ! መቼም ተውሾች ጋር እየተሯሯጠ አውሬና ጠላት ይከላከላል
አይባል ይኑር ከተባለ ወገኑ ከማን ነው? ተከብቶቹ ወይንስ ከእኛ! አሉ ከወደመሀል መፋቂያቸውን ሲያኝኩ የቆዩት ሽማግሌ
"ጥሩ ነው የሁላችሁም አስተያየት አዲስ ነገር መምጣቱ ይኸው ሁለት ሶስት ቦታ ከፋፍሎ አጨቃጨቀን ያልነበረ ነገር
ሲመጣ ያልነበረ ችግር ይፈጥራል ነጯ ሐመር የእኛ የሆነች እንግዳ ናት መሂና ያለችውን አውሬ ዱካውን ለማጥፋት በጥይትና ጦር
ደብድበን እንቅበረው ብንል እሷን እናሳዝናት ይሆናል"
ባይሆን አውሬሽን ካመጣሽበት ጫካ ጥለሽ ነይ ብንላት አይሻልም
ወንድሞቼ!" አሉ። አንተነህ ይመር ጋልታምቤ ጎን የተቀመጡት ሽማግሌ
ተው! ተው! ይህችን ሰው ተማበራችን አታውጧት! እሷ
ሐመር ናት የሐመር ልጃገረድ ተቀብላማ እንደ እህቶችዋ የፍየል ቆዳ ለብሳ ለዘመዷ ለከሎ ከብት
የአባቷን ትክክለኛ ደንብ
ዝላይ ተገርፋ … እንዴት እንዴት ነው እንደውጭ ሰው ይከፋታል ማለት! ከአባትሽ ባህልና ደንብ ውጭ ያመጣሽው አውሬ ቦርጆን ያስከፋል የአባቶቻችንንም ነፍስ ያሳዝናል እነሱ ተቆጥተው ዝናብ ከሚያጠፉብን በሽታ ከሚልኩብን አውሬሽን ቀብረነው እንረፍ
ብንላት በፍጡም አይከፋትም ወዲያውስ ከሽማግሌ ቃል ወጥታ የት ልትደርስ ኧረ አይከፋትም!" አሉ የዘርሲዎች አለቃ ከዚያ ለረጅም ጊዜ ዝምታ ሰፍኖ ቆየ
"ጥሩ ነው! እንዳላችሁትም
ነጯ ሐመር የእኛ ናት, የእኛ
ያልሆነውን ግን ዝም ብለን ብንለቀው ምን እንደሚያመጣ አናውቅም ሲቆይ ልጆቻችንን እሷን ጨምሮ: እኛን ይተናኮስ
አይተናኮስ ሳናውቅ እናጥፋው እስከተባባልን
ድረስ በኋላ ለቀን
ከምናሳድድ እዚሁ ገራም መስሎ አጠገባችን እንዳለ አድብቶ በጥይት ማጎን ነው የሚበጀው ካለበለዚያ
እኮ አስተውላችሁት እንደሁ
አላውቅም እንጂ አጉረምርሞ አጉረምርሞ ሰውነቱ የጋለ እንደሆን
እንደ ጥይት ከተፈተለከ
ድንጋይ አይል ውሃ ... ማን ጀግና ያቆመዋል! ስለዚህ ሳይደነብር አዋዝተው ጎረምሶች በክላሽ ጥይት
ሆድቃውን እንዲነድሉት ማድረግ ነው"" እንዳሉ
"ይህስ እውነት ነው! በቀደም ሳላየው ሩም … ብሎ ባጠገቤ ቢያልፍ የድምፁ ወላፈን እንዴት አሽቀንጥሮ ወረወረኝ መሰላችሁ ተዚያ ንዴቱ ይሁን ድንጋጤው ሰማይ እሆን ምድር ጠፋኝ!" አሉ ሌላው አዛውንት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አራት
ዘርሲዎች ግማሽ ክብ ሰርተው ከመንደሩ ራቅ ብላ ዙሪያ ገቡን ከምታሳየው
የግራር ዛፍ ስርቁጭ ብለዋል ጩሉሌዎች
አንገታቸውን ቁልቁል ደፋ አድርገው በዛ ዙሪያ ያንዣብባሉ: ነፋሱ
ቅጠሎችን ጎንበስ ቀና እያደረገ ይነፍሳል
ከፊት ለፊታቸው ርጥብ
ቅጠል ተነጥፏል መሃል ላይ ጎረምሶች የተጠበሰውን የፍየል ስጋ እየቆራረጡ የፍሪንባውን ሥጋ በእድሜ ለገፉትና በጀግንነታደው ለሚታወቁት ለሌሎች ደግሞ ከተለያየውደ የስጋ አይነት እፊት ለፊታቸው ካለው ቅጠል አስቀመጡ" ህፃናት ጨዋታቸውን አቁመው ራቅ ብለው ሲቁለጨለጩ ቆይተው እደላው አልቆ መብሉ ሲጀመር ወደየአባቶቻቸው ጉያ ተሸጉጠው ዳረጎታቸውን እየተቀበሉ ከአጥንት ጋር መታገል ጀመሩ በመጨረሻ የሚበላው ከተበላ: ቀሪውን ደግሞ ጎረምሶቹ ካቀለጣጠፉት በኋላ ወጣቶቹ ቅጠሉን ሰብስበው ጥለው
ከስብሰባው አካባቢ ርቀው ሄዱ።
የሽማግሎች አለቃ ጦራቸውን ይዘው ከተቀመጡበት ተነስተው
ከፈርሱ እግራቸውን ቀባ አድርገው ወዲህ ወዲያ ወዲያ ወዲህ አሉና፣
"የአባት ደንብ ጥሩ ነው" በልክ መብላት የአባቶቻችን ባህል ነው አባቶቻችን የራበውና የጠገበ ትክክል ፍርድ አይሰጥም ይሉ
ነበር" የጠገበ ወንድ ሴት ማለት ነው መሳቅ ቧልት ይወዳል ከብቶችን አይፈቅድም ጫካውን አይቃኝም ከጓደኞቹ ጋር
አይመክርም መዝለል አይችልም መቀመጥና ማንጎላጀት ይወዳል
ትክክለኛ ፍርድ በዚህ ምክንያት አይሰጥም ይሉ ነበር አባቶቻችን" ሽማግሌው እቱፍ: እቱፍ
ብለው የጦሩን ዘንግ በምራቃቸው ቀባ ቀባ እያደረጉ ሽማግሎችን:
የአባታቸውን አገር አድማስ እየተዟዟሩ አይተው
አባቶቼ የራበውም ከጠገበ አይሻልም ይሉ ነበር የራበው ሰው ሰነፍ ነው
ሲኖረው አያውቅበትም
የወደቀችው ጀንበር:
የጠፋችው ጨረቃ ተመልሰው የሚመጡ
አይመስሉትም እንደ
አጋሰስ ፈረስ ዘመዶቹ ለመቋቋሚያ የሰጡትን ፍየሉንም፥ በጉንም
ከብቱንም: እህሉንም ብቻውን እየበላ ነገን ዘንግቶ: ልጆቼ: የአባቴ
ምክር ሳይል ሁሉን ያሟጥጥና የሚያልበው ሲያጣ የሚበላው
ሲቸግረው ሰውን: መሬቷን: ቦርጆን: አባቶቹን ይራገማል" ሆዱን
ለመሙላት ይቀማል ይዋሻል … ፍቅር አያውቅም ዘመድ ወገን አይለይም
አያስተውልም፤ ጨካኝ ነው
በዚህ ምክንያት
አባቶቻችን የራበው ሰው ትክክል አይፈርድም ይሉ ነበር አባቶቻችን ትክክል ናቸው ወንድሞቼ ጥጋብ ልቦናን ያዛባል ረሃብ ደግሞ ተስፋ መቁረጥንና ጥላቻን ያመጣል ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ ሁለቱም ያስዋሻሉ" ብለው በርኮታቸው ላይ ቁጭ አሉ
ዝምታው ቀጠለ ሐመር ላይ ተረትን ሽማግሌ ለሌላው ማስታወስ እንጂ አይጨርሰውም የሰሙት እኩል: የፈፀሙት እኩል … ስለሆነ ተረት ጨራሽ አዳማጭ የለውም"
"በሉ ተናገሩ?" አሉ ሽማግሌው ከጥቂት ቆይታ በኋላ ጥሩ ነው! ከወደ መሃል አንዱ ድምፅ አሰሙ ገልመጥ ብሎ ያዬ የለም ሁሉም ግን አባባላቸውን በጆሮው ቀልቧል።
"ጥሩ ነው!- በአካል ተለይተውን ነፍሶቻቸው ደንቡን ጥበቃ አብረውን ላሉት ወንድሞቻችን ተገቢው ደንብ የሚሰራበት
ቀን ይመረጥ ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው በየበረሃው የአሉትን ተባት በግና ፍየሎች ከብቶችን ያስመጡ" በየመንደሩ ለሚኖሩት ዘመድ ጓደኞችም ጥሪ ይላክ ለዚያ ደሞ ዛሬ ቀኑ ተቆርጦ ቋጠሮ ይዘጋጅ አሉ።
የሽማግሎች አለቃ ሌላ ኃሳብ አለመኖሩን በዝምታደ ጠበቁና አንድ ጎረምሳ ጠርተው ልጥ አምጣ አንተ" አሉት ልጡ መጣ
"ስንት ላይ ይቋጠር?"
"መከን ተቢ" አሉ አንድ ሽማግሌ በስተግራ በኩል
ከተቀመጡት ሰላሳ ለማለት ልጡ ሰላሳ ላይ ተቋጥሮ ለሟቹ ታናሽ ወንድም
ተሰጠው" የሽማግሎች አለቃ አንዱን ችግር
በመቋጨታቸው
"ባይሮ ኢሜ" አሉ ሽማግሎችን እግዜር
ይስጣችሁ ለማለት
"በሉ ቀጥሉ?" አሉ የስብሰባው መሪ
"ጥሩ ነው!" አለ ልጅ እግሩና የአባቱን ጠላት ገሎ በቅርቡ
ከሽማግሌዎች ጋር ለመቀመጥ እድል ያገኘው ሰለምቤ፤ "ጥሩ ነው!
ታለውሻ በቀር አባቶቻችን ከአውሬ ጋር አልኖሩም እና ካርለቴ ይዛብን የመጣችውን አውሬ በጥይት አጉኖ ራቅ አድርጎ መቅበር ነው "አለ ገና የጎረምሳነት ባህሪው ሙሉ በሙሉ ያልቀዘቀዘለት ወጣቱ ሽማግሌ አለመብሰሉ በአነጋገሩ ፍጥጥ ብሎ እየታየበት።
"ጥሩ ነው! አውሬ ማለት ከብት የሚበላ ችግር የሚፈጥር ነው የነጯ ሐመር የካርለቴ አራት እግር አውሬ ሳይሆን መሂና
ነው የሚባል አባቶቻችን ደሞ መሂና የሚባል አውሬ አለ አላሉንም ደሞስ የካርለቴ መሂና እንደ ፈረስ እየጫነን ገበያ እያመላለሰን ነው እና መኖሩ ምን ጎዳ! አሉ ግራሯን የተደገፉት አንድ ዐይና
የአባት ደንብ እየሻርን ያ ይጎዳል ይሄ ይጠቅማል
ካልንማ ይህች አገርና ይህ ህዝብ መዓት ይመጣበታል" በነሱ ጊዜ ያልነበረ አውሬ አሁንም መኖር የለበትም " አሉ አገጫቸውን በግራ
እጃቸው ደግፈው የቆዩት ሽማግሌ ከዚያ ክርክሩ ከተለያዬ አቅጣጫ
መቅረቡ ቀጠለ
በአባቶቻችን ደንብ ፍየል ቢመጣ ፍየል ጋጥ: ከብት
ቢመጣ ከብቶች በረት ሰው ቢመጣ ወደ ሰዎች መኖሪያ ጎጆ ይገባል እህ እንዲህ እስተሆነ ድረስ የካርለቴ መሂና የሚገባ
ፍየሎች ጋጥ ነው? ከከብቶች በረት ነው? ወይንስ ከሰዎች ጋር ጎጆ
ውስጥ! መቼም ተውሾች ጋር እየተሯሯጠ አውሬና ጠላት ይከላከላል
አይባል ይኑር ከተባለ ወገኑ ከማን ነው? ተከብቶቹ ወይንስ ከእኛ! አሉ ከወደመሀል መፋቂያቸውን ሲያኝኩ የቆዩት ሽማግሌ
"ጥሩ ነው የሁላችሁም አስተያየት አዲስ ነገር መምጣቱ ይኸው ሁለት ሶስት ቦታ ከፋፍሎ አጨቃጨቀን ያልነበረ ነገር
ሲመጣ ያልነበረ ችግር ይፈጥራል ነጯ ሐመር የእኛ የሆነች እንግዳ ናት መሂና ያለችውን አውሬ ዱካውን ለማጥፋት በጥይትና ጦር
ደብድበን እንቅበረው ብንል እሷን እናሳዝናት ይሆናል"
ባይሆን አውሬሽን ካመጣሽበት ጫካ ጥለሽ ነይ ብንላት አይሻልም
ወንድሞቼ!" አሉ። አንተነህ ይመር ጋልታምቤ ጎን የተቀመጡት ሽማግሌ
ተው! ተው! ይህችን ሰው ተማበራችን አታውጧት! እሷ
ሐመር ናት የሐመር ልጃገረድ ተቀብላማ እንደ እህቶችዋ የፍየል ቆዳ ለብሳ ለዘመዷ ለከሎ ከብት
የአባቷን ትክክለኛ ደንብ
ዝላይ ተገርፋ … እንዴት እንዴት ነው እንደውጭ ሰው ይከፋታል ማለት! ከአባትሽ ባህልና ደንብ ውጭ ያመጣሽው አውሬ ቦርጆን ያስከፋል የአባቶቻችንንም ነፍስ ያሳዝናል እነሱ ተቆጥተው ዝናብ ከሚያጠፉብን በሽታ ከሚልኩብን አውሬሽን ቀብረነው እንረፍ
ብንላት በፍጡም አይከፋትም ወዲያውስ ከሽማግሌ ቃል ወጥታ የት ልትደርስ ኧረ አይከፋትም!" አሉ የዘርሲዎች አለቃ ከዚያ ለረጅም ጊዜ ዝምታ ሰፍኖ ቆየ
"ጥሩ ነው! እንዳላችሁትም
ነጯ ሐመር የእኛ ናት, የእኛ
ያልሆነውን ግን ዝም ብለን ብንለቀው ምን እንደሚያመጣ አናውቅም ሲቆይ ልጆቻችንን እሷን ጨምሮ: እኛን ይተናኮስ
አይተናኮስ ሳናውቅ እናጥፋው እስከተባባልን
ድረስ በኋላ ለቀን
ከምናሳድድ እዚሁ ገራም መስሎ አጠገባችን እንዳለ አድብቶ በጥይት ማጎን ነው የሚበጀው ካለበለዚያ
እኮ አስተውላችሁት እንደሁ
አላውቅም እንጂ አጉረምርሞ አጉረምርሞ ሰውነቱ የጋለ እንደሆን
እንደ ጥይት ከተፈተለከ
ድንጋይ አይል ውሃ ... ማን ጀግና ያቆመዋል! ስለዚህ ሳይደነብር አዋዝተው ጎረምሶች በክላሽ ጥይት
ሆድቃውን እንዲነድሉት ማድረግ ነው"" እንዳሉ
"ይህስ እውነት ነው! በቀደም ሳላየው ሩም … ብሎ ባጠገቤ ቢያልፍ የድምፁ ወላፈን እንዴት አሽቀንጥሮ ወረወረኝ መሰላችሁ ተዚያ ንዴቱ ይሁን ድንጋጤው ሰማይ እሆን ምድር ጠፋኝ!" አሉ ሌላው አዛውንት
👍21
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
ካለወትሮው እያከታተለ የሚወርደው ዝናብ የሐመርን ምድር:
የወሮን መንደር የብርሃን ጥላ አልብሷታል" ሰማዩ ላይ በጨርቅ እንደተጠቀለለ ህፃን ዳመናው እየተገለባበጠ
ምርር ብሎ እየጮኸ
ብልጭታው በሁሉም አቅጣጫ ይፈነጣጠቃል
ከክቧ የሐመሮች ጎጆ የሚትጎለጎለው
ከሚጥመለመለው ጥቁር ዳመና ጋር እየተደባለቀ ይጠፋል ፍየሎች በጎች ጥጆች ገና ከበረታቸው አልወጡም በከብቶች አንገት የተንጠለጠለው የኤሊ ድንጋይ ከብቶቹ በተንቀሳቀሱ ቁጥር
ቋቋ ቋቋ እያለ ይሰማል" መንደሯ ልብ ብለው ሲያዳምጧት ትንፋሽዋ እንደወትሮዋ ነው፤ ማነጠሱ፥ ጨዋታው፥ እንጉርጉሮው: ቀልዱ ወፍጮው፥ የወፎቹ ዝማሬ ሁሉም ከዘመናት በፊት
እንደተቃኘው ነው
የናት ጉያ ሙቀት የናፈቃቸው ሆዳቸውን የሞረሞራቸው ጥጆች ግን ከናታችን አራክቡን በሚል ሆድን በሚያላውስ ቅላፄ እ-
ም--ዋ … እም-ቡ-ዋ እያሉ የጌቶቻቸውን ጆሮና ቀልብ ለመሳብ ረሃብና ናፍቆታቸውን በለሆስታ ዜማ አለዝበው ያንጎራጉራሉ" ላሞች እንደሌሎች ከብቶች ማመንዠካቸውን አቁመው ፊታቸውን ወደ ጥጆቻቸው አዙረው ዐይናቸውን እያቁለጨለጩ: ሳጋቸውን እያሰሙ የጥጆችን ከለላ በአፍንጫቸው እያሸተቱና
እየነካኩ የናትነት አንጀታቸው ረፍት ነስቶ ያንሰፈስፋቸዋል አንተነህ ይመር ከምድጃው ጎን ካለችው ትንሽ መደብ ላይ
በቦርኮታው የቀኝ ጭኑን አስደግፎ፥ ጎኑን እሳቱን እያሞቀ እሱም
የማይሰማ ውስጡ ፈልቶ እዚያው ተኖ የሚቀረውን ሳጉን ራሱ ለራሱ ይሰማል
ባለቤቱ እሳቱን እየቆሰቆሰች ሻላው (ቆጡ) ላይ ባሰረችው ጠፍር የአንጠለጠለችውን እርጎ በቀኝ እጅዋ ወደ ፊትና ኋላ
ትንጣለች ቅቤ ለማውጣት ነጭና ጥቁር መልክ ያለው ቁርበት ከበስተ ኋላዋ ተነጥፏል ዳሚ ሰረቅ እያደረገች ስታየው ቆይታ
"ይእ! ምን ሆነሃል የኔ ጌታ?" አለችው
ቢጨንቃት" እሱ ግን ዝም አላት ዝም እየተነፈሰ ጭጭ
"ተቡኑ ልስጥህ?"
ጋልታምቤ መልስ ሳይሰጣት ውጭውን
አየው በጠባቧ በር በግድግዳው ቀዳዳ አየሩ ክርስስ ያለ ነው ቀዝቃዛ የሱም ልብ ቀዝቅዛለች
በሐመር ባህል የተጠየቀ ሁሉ ወዲያው የመመለስ ግዴታ የለበትም አዋቂ አስተሳሰቡ የበሰለ ከመናገሩ በፊት ልቡን ዐይኑ ላይ ማውጣት አለበት በልቦናው የሚያይ ሐሳቡ ሚዛናዊ ሆነ ክፉና ደግ ለመለየት በቃ ሃላፊነት ለመቀበል ደረሰ ማለት ነው" ጋልታምቤም በዚህ መላ
የሚስቱን ጥያቄና ጭጋጋማውን ቀን በልቦናው አየው" ልቦናው ግን ምንም እንዲል አልፈቀደለትም
ዝምታ ደግሞ በራሱ ቋንቋ ነው ዝምታና ዐይን ዝምታና ጥርስ ዝምታና ዝም በአይነቱ የተለያዬ ትርጉም አላቸው በቢጫው በሬ ምድር በሐመር።
ዳሚ የጋልታምቤን ዝምታና ዐይን አይታ የሚያሳስበው ነገር እንዳለ አውጥቶ ሊነግራት ግን እንዳልፈለገ ተረዳች ያን ጊዜ።
ይእ! ምን ሆነ? እንግዲ ተሱ ይምጣ'ንጂ እኔ ምናባቴ
ላርግለት ብላ እሷም ዝም አለች ዝም ተባባሉ እሱና እሷ እሱና እሱ: እሱና ተፈጥሮ ተዘጋጉ"
ጋልታምቤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሰረቅ አድርጎ አያት ልቧን ከንፈሯ ላይ ተቀምጦ አየው ፍርሃት ነፋ ልትት፤ ነፋ ልትት
ሲያደርገው ሲገፋፋው ሲያንቀጠቅጠው ሲያወዛውዘው ተመለከተው
ዳሚ ከበስተግራዋ ተሰካክተው ከተቀመጡት በጨሌ ያጌጠውን
ሾርቃ አንስታ ጠረግ ጠረግ በማድረግ ከተወዘተው እንስራ በቅል ጭልፋ ሸፈሮ ቡና ቀድታ አቀበለችው
ጋልታምቤ እግሩን አንፈራጦ ተቀበላትና ግራ ቀኝ ፊትና ኋላ ጎለል ጎለል አድርጎ አበረደው ከዚያ እፉት ብሎ ፕስስ አድርጎ አማተበ ሸፈሮ ቡና የቦርጆ ፍሬ ሽፋን ነው ደስታን ያመጣል ራስን ለማየት ከራስ ጋር ለመምከር የቆሸሸ ህሊናን
ፈውስን ለማጽዳት የሚፋጅ የሚያቃጥል ነገር ሲያጋጥም ነቅነቅ ወዝወዝ
እያደረጉ ለማብረድ ለማቀዝቀዝ ጥሩ ነው
ይህ ሐይል ያለው
ሸፈሮ የተወጠረውን ስሜት ሲያላላው፥ የታመቀ
የጋልታምቤን ትንፋሹን እያንቦለቦለ አስወጥቶ እሁ! አለ ዳሚ አየችው የደሙ
ዝውውር ተረጋግቶ ይሽከረከራል: ገፅታው ጠይቂኝ ይላል"
"ዛሬ ቀን ምን ሆነሃል?" ስትለው ትክ ብሎ አያትና ዐይኖቹን ከላይዋ ላይ አንስቶ ከራሱ ጋር ሙግት ገጠመ" ይህች ሰው
ባትሰማው ይሻል ይሆን? ይህማ የማይቀር እዳዋ ነው ከሌላ ከምትሰማው እኔ ብነግራት አይሻልም አአይ ይቅርባት ትጨነቃለች ችግሩ ደግሞ ወደሷ እየገሰገሰ ነው መከራዋን በቀስ እየደራረበች ብትሸከመው አይሻልም … ብሎ ፊቱን ወደ ዳሚ
መለሰው
"ዳሚ!"
"ዬ!" አለችው ዐይኖችዋን ከዐይኑ ነቅላ እሳት እሳቱን እያየች አይን አፋርነቷ
ትልቁ ውበቷ ነው" ሁሌም ሲጠራት ዐይኗ
ይንከራተትና የሆነ ቦታ ገብቶ ውሽቅ ይላል" የምታየው ግን እሱን ነው።
"ዳሚ!" አላት ደግሞ
"ዬ!" አለችው ድምጿን ከረር አድርጋ እየሰማሁህ ነው'
ለማለት።
"ያች ልጅ መንጠፏ ነው ይሆን?" አላት የሃሣብ ሸክሙን በጥሶ ላይዋ ላይ በትኖ ዳሚ ጥያቄውን ስትሰማ ህሊናዋ አስደንጋጭ ነጎድጓድ ባረቀበት ክው ብላ ደነገጠች አልጮኸችም መልስም አልሰጠችም ውስጧ ግን ባንዴ ባዶ ሆነ ቀፎ ዐይኖችዋን እሳቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ተክላ ቆየች
ጥያቄው በቀፎው ሰውነቷ
እየተንጎዳጎደ ነዘራት አመማት እንደ ሚጥሚጣ ለበለባት ... እሳቱ
ላይ የተሰካው ዐይኗ ሙቀቱ እንዳቀለጠው ሁሉ በፈሳሽ ተሞላ በእንባ በምሬት የዐይኗ ኳስ ሲንቀሳቀስ ግን እንባዋ ፈሰሰ እንባዋን ንፍጧ ጠርቶት ቁልቁል ወረደ እንባዋ ንፍጧን ተከተለው አያት ጋልታምቤ እንደገና በዐይነ-ህሊናው ራሱን አየው፤ እንደ
ከስኬ ወንዝ ወደ ውስጡ የሚሰርገው እንባው ስለማይፈስ መውጫ
ስለሌለው የሰራ አካላቱ ላይ የእንባ ጎርፍ ተኝቶበታል"
"ሁለት ዓመት ሙሉ ይኸው ወልዳ ለመሳም አልታደለችም የሐመር ሽማግሎችም ተነጠፈች በሐመር ደንብ መሰረት ለከሎ ወይ ምትክ ይሰጠው ካለበለዚያም ጥሎሹ ይመለስ እያሉ ነው" አላትና
መሬቷን ተመለከታት ዳሚ የሚለውን አልሰማችውም ከፊት ለፊቱ ተቀምጣ እሷ ግን የለችም አትንቀሳቀስም:
ጋልታምቤ ከውስጥ የዳሚ ከውጭ የላሞች ሳግ ተሰማው የጥጆች ጥሪ የጎይቲ ሰቆቃ
መሀን ሴት በሐመር ልቧ እንደ አሮጌ ቅል የተጠረማመሰ ምስጥ እንዳነካከተው ግንድ ተስፋዋ ፍርክስክስ ያለ ከዚህ መከራዋ በተጨማሪም ቤተሰቧን የመጥፎ ቤተሰብ የምታሰኝ እሷ የመጣችበትን መንገድ ለሌላው ግን የምትከለክል
እርጉም ተብላ
ከማህበራዊው ቡድን ተነጥላ ተወርውራ የምትጣል የቤተሰቧን ጎጆ
በጨለማ የምትሸፍን ናት
"የፈራሁት ደረሰ! ብላ ዳሚ የእንባዋን ውታፍ ከፈተችው
ልቧን ነደለችው ሆን ብላ ያዳፈነችውን የጭንቀት እሳት እፍ አለችው የእንባ ፈሳሽ ያገኘው ስሜቷ እንደ ደረቀ ቅጠል በውስጧ
ሲንቀለቀል ናጣት አርገፈገፋት አስቃሰታት
ስለዚህ ጋልታምቤ ጭንቀቷን ተቀምጦ ማየት ሰቀጠጠው
ከተቀመጠበት ተነስቶ ጥጆችን ከእናታቸው ያራክባቸዋል ከጥቂት ደቂቃ በኋላ አንዱ ጠብቶ ሌላው
ሊያራክባቸው ወጣ ጥጆችን
አጥብቶ ጥጋብ ይሆንና የመለያየቱ ምልክት ድራሹ ጠፍቶ መላላስና
መቦረቅ ይመጣል አንተነህ ይመር ለጎይቲ ምኑን አጥብቶ ከጭንቀቷ
ይገላግላታል! አለኝታው፡ መስታዋቱ ደስታውን እንዳያይባት መከራ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
ካለወትሮው እያከታተለ የሚወርደው ዝናብ የሐመርን ምድር:
የወሮን መንደር የብርሃን ጥላ አልብሷታል" ሰማዩ ላይ በጨርቅ እንደተጠቀለለ ህፃን ዳመናው እየተገለባበጠ
ምርር ብሎ እየጮኸ
ብልጭታው በሁሉም አቅጣጫ ይፈነጣጠቃል
ከክቧ የሐመሮች ጎጆ የሚትጎለጎለው
ከሚጥመለመለው ጥቁር ዳመና ጋር እየተደባለቀ ይጠፋል ፍየሎች በጎች ጥጆች ገና ከበረታቸው አልወጡም በከብቶች አንገት የተንጠለጠለው የኤሊ ድንጋይ ከብቶቹ በተንቀሳቀሱ ቁጥር
ቋቋ ቋቋ እያለ ይሰማል" መንደሯ ልብ ብለው ሲያዳምጧት ትንፋሽዋ እንደወትሮዋ ነው፤ ማነጠሱ፥ ጨዋታው፥ እንጉርጉሮው: ቀልዱ ወፍጮው፥ የወፎቹ ዝማሬ ሁሉም ከዘመናት በፊት
እንደተቃኘው ነው
የናት ጉያ ሙቀት የናፈቃቸው ሆዳቸውን የሞረሞራቸው ጥጆች ግን ከናታችን አራክቡን በሚል ሆድን በሚያላውስ ቅላፄ እ-
ም--ዋ … እም-ቡ-ዋ እያሉ የጌቶቻቸውን ጆሮና ቀልብ ለመሳብ ረሃብና ናፍቆታቸውን በለሆስታ ዜማ አለዝበው ያንጎራጉራሉ" ላሞች እንደሌሎች ከብቶች ማመንዠካቸውን አቁመው ፊታቸውን ወደ ጥጆቻቸው አዙረው ዐይናቸውን እያቁለጨለጩ: ሳጋቸውን እያሰሙ የጥጆችን ከለላ በአፍንጫቸው እያሸተቱና
እየነካኩ የናትነት አንጀታቸው ረፍት ነስቶ ያንሰፈስፋቸዋል አንተነህ ይመር ከምድጃው ጎን ካለችው ትንሽ መደብ ላይ
በቦርኮታው የቀኝ ጭኑን አስደግፎ፥ ጎኑን እሳቱን እያሞቀ እሱም
የማይሰማ ውስጡ ፈልቶ እዚያው ተኖ የሚቀረውን ሳጉን ራሱ ለራሱ ይሰማል
ባለቤቱ እሳቱን እየቆሰቆሰች ሻላው (ቆጡ) ላይ ባሰረችው ጠፍር የአንጠለጠለችውን እርጎ በቀኝ እጅዋ ወደ ፊትና ኋላ
ትንጣለች ቅቤ ለማውጣት ነጭና ጥቁር መልክ ያለው ቁርበት ከበስተ ኋላዋ ተነጥፏል ዳሚ ሰረቅ እያደረገች ስታየው ቆይታ
"ይእ! ምን ሆነሃል የኔ ጌታ?" አለችው
ቢጨንቃት" እሱ ግን ዝም አላት ዝም እየተነፈሰ ጭጭ
"ተቡኑ ልስጥህ?"
ጋልታምቤ መልስ ሳይሰጣት ውጭውን
አየው በጠባቧ በር በግድግዳው ቀዳዳ አየሩ ክርስስ ያለ ነው ቀዝቃዛ የሱም ልብ ቀዝቅዛለች
በሐመር ባህል የተጠየቀ ሁሉ ወዲያው የመመለስ ግዴታ የለበትም አዋቂ አስተሳሰቡ የበሰለ ከመናገሩ በፊት ልቡን ዐይኑ ላይ ማውጣት አለበት በልቦናው የሚያይ ሐሳቡ ሚዛናዊ ሆነ ክፉና ደግ ለመለየት በቃ ሃላፊነት ለመቀበል ደረሰ ማለት ነው" ጋልታምቤም በዚህ መላ
የሚስቱን ጥያቄና ጭጋጋማውን ቀን በልቦናው አየው" ልቦናው ግን ምንም እንዲል አልፈቀደለትም
ዝምታ ደግሞ በራሱ ቋንቋ ነው ዝምታና ዐይን ዝምታና ጥርስ ዝምታና ዝም በአይነቱ የተለያዬ ትርጉም አላቸው በቢጫው በሬ ምድር በሐመር።
ዳሚ የጋልታምቤን ዝምታና ዐይን አይታ የሚያሳስበው ነገር እንዳለ አውጥቶ ሊነግራት ግን እንዳልፈለገ ተረዳች ያን ጊዜ።
ይእ! ምን ሆነ? እንግዲ ተሱ ይምጣ'ንጂ እኔ ምናባቴ
ላርግለት ብላ እሷም ዝም አለች ዝም ተባባሉ እሱና እሷ እሱና እሱ: እሱና ተፈጥሮ ተዘጋጉ"
ጋልታምቤ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሰረቅ አድርጎ አያት ልቧን ከንፈሯ ላይ ተቀምጦ አየው ፍርሃት ነፋ ልትት፤ ነፋ ልትት
ሲያደርገው ሲገፋፋው ሲያንቀጠቅጠው ሲያወዛውዘው ተመለከተው
ዳሚ ከበስተግራዋ ተሰካክተው ከተቀመጡት በጨሌ ያጌጠውን
ሾርቃ አንስታ ጠረግ ጠረግ በማድረግ ከተወዘተው እንስራ በቅል ጭልፋ ሸፈሮ ቡና ቀድታ አቀበለችው
ጋልታምቤ እግሩን አንፈራጦ ተቀበላትና ግራ ቀኝ ፊትና ኋላ ጎለል ጎለል አድርጎ አበረደው ከዚያ እፉት ብሎ ፕስስ አድርጎ አማተበ ሸፈሮ ቡና የቦርጆ ፍሬ ሽፋን ነው ደስታን ያመጣል ራስን ለማየት ከራስ ጋር ለመምከር የቆሸሸ ህሊናን
ፈውስን ለማጽዳት የሚፋጅ የሚያቃጥል ነገር ሲያጋጥም ነቅነቅ ወዝወዝ
እያደረጉ ለማብረድ ለማቀዝቀዝ ጥሩ ነው
ይህ ሐይል ያለው
ሸፈሮ የተወጠረውን ስሜት ሲያላላው፥ የታመቀ
የጋልታምቤን ትንፋሹን እያንቦለቦለ አስወጥቶ እሁ! አለ ዳሚ አየችው የደሙ
ዝውውር ተረጋግቶ ይሽከረከራል: ገፅታው ጠይቂኝ ይላል"
"ዛሬ ቀን ምን ሆነሃል?" ስትለው ትክ ብሎ አያትና ዐይኖቹን ከላይዋ ላይ አንስቶ ከራሱ ጋር ሙግት ገጠመ" ይህች ሰው
ባትሰማው ይሻል ይሆን? ይህማ የማይቀር እዳዋ ነው ከሌላ ከምትሰማው እኔ ብነግራት አይሻልም አአይ ይቅርባት ትጨነቃለች ችግሩ ደግሞ ወደሷ እየገሰገሰ ነው መከራዋን በቀስ እየደራረበች ብትሸከመው አይሻልም … ብሎ ፊቱን ወደ ዳሚ
መለሰው
"ዳሚ!"
"ዬ!" አለችው ዐይኖችዋን ከዐይኑ ነቅላ እሳት እሳቱን እያየች አይን አፋርነቷ
ትልቁ ውበቷ ነው" ሁሌም ሲጠራት ዐይኗ
ይንከራተትና የሆነ ቦታ ገብቶ ውሽቅ ይላል" የምታየው ግን እሱን ነው።
"ዳሚ!" አላት ደግሞ
"ዬ!" አለችው ድምጿን ከረር አድርጋ እየሰማሁህ ነው'
ለማለት።
"ያች ልጅ መንጠፏ ነው ይሆን?" አላት የሃሣብ ሸክሙን በጥሶ ላይዋ ላይ በትኖ ዳሚ ጥያቄውን ስትሰማ ህሊናዋ አስደንጋጭ ነጎድጓድ ባረቀበት ክው ብላ ደነገጠች አልጮኸችም መልስም አልሰጠችም ውስጧ ግን ባንዴ ባዶ ሆነ ቀፎ ዐይኖችዋን እሳቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ተክላ ቆየች
ጥያቄው በቀፎው ሰውነቷ
እየተንጎዳጎደ ነዘራት አመማት እንደ ሚጥሚጣ ለበለባት ... እሳቱ
ላይ የተሰካው ዐይኗ ሙቀቱ እንዳቀለጠው ሁሉ በፈሳሽ ተሞላ በእንባ በምሬት የዐይኗ ኳስ ሲንቀሳቀስ ግን እንባዋ ፈሰሰ እንባዋን ንፍጧ ጠርቶት ቁልቁል ወረደ እንባዋ ንፍጧን ተከተለው አያት ጋልታምቤ እንደገና በዐይነ-ህሊናው ራሱን አየው፤ እንደ
ከስኬ ወንዝ ወደ ውስጡ የሚሰርገው እንባው ስለማይፈስ መውጫ
ስለሌለው የሰራ አካላቱ ላይ የእንባ ጎርፍ ተኝቶበታል"
"ሁለት ዓመት ሙሉ ይኸው ወልዳ ለመሳም አልታደለችም የሐመር ሽማግሎችም ተነጠፈች በሐመር ደንብ መሰረት ለከሎ ወይ ምትክ ይሰጠው ካለበለዚያም ጥሎሹ ይመለስ እያሉ ነው" አላትና
መሬቷን ተመለከታት ዳሚ የሚለውን አልሰማችውም ከፊት ለፊቱ ተቀምጣ እሷ ግን የለችም አትንቀሳቀስም:
ጋልታምቤ ከውስጥ የዳሚ ከውጭ የላሞች ሳግ ተሰማው የጥጆች ጥሪ የጎይቲ ሰቆቃ
መሀን ሴት በሐመር ልቧ እንደ አሮጌ ቅል የተጠረማመሰ ምስጥ እንዳነካከተው ግንድ ተስፋዋ ፍርክስክስ ያለ ከዚህ መከራዋ በተጨማሪም ቤተሰቧን የመጥፎ ቤተሰብ የምታሰኝ እሷ የመጣችበትን መንገድ ለሌላው ግን የምትከለክል
እርጉም ተብላ
ከማህበራዊው ቡድን ተነጥላ ተወርውራ የምትጣል የቤተሰቧን ጎጆ
በጨለማ የምትሸፍን ናት
"የፈራሁት ደረሰ! ብላ ዳሚ የእንባዋን ውታፍ ከፈተችው
ልቧን ነደለችው ሆን ብላ ያዳፈነችውን የጭንቀት እሳት እፍ አለችው የእንባ ፈሳሽ ያገኘው ስሜቷ እንደ ደረቀ ቅጠል በውስጧ
ሲንቀለቀል ናጣት አርገፈገፋት አስቃሰታት
ስለዚህ ጋልታምቤ ጭንቀቷን ተቀምጦ ማየት ሰቀጠጠው
ከተቀመጠበት ተነስቶ ጥጆችን ከእናታቸው ያራክባቸዋል ከጥቂት ደቂቃ በኋላ አንዱ ጠብቶ ሌላው
ሊያራክባቸው ወጣ ጥጆችን
አጥብቶ ጥጋብ ይሆንና የመለያየቱ ምልክት ድራሹ ጠፍቶ መላላስና
መቦረቅ ይመጣል አንተነህ ይመር ለጎይቲ ምኑን አጥብቶ ከጭንቀቷ
ይገላግላታል! አለኝታው፡ መስታዋቱ ደስታውን እንዳያይባት መከራ
👍30
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ካርለት ድንኳናን ዘግታ ስትፅፍ የሰው ኮቴ የሰማች መሰላትና ጆሮዋን አቁማ አዳመጠች
"ካርለት?"
"የስ" ብላ ቶሎ በማስተካከል "ዬ! አለች - እንደ ሐመር ልጃገረዶችı ካርለት የጠራት ሰው ማን እንደሆነ አውቃዋለች
ደልቲ ነው ቀብራራው ጀግና የድንኳኗን ዚፕ ከፍታ ፈገግ ብላ አየችው" ሰውነቱ በአኖ (ከኦሞ ወንዝ ዳር በመጣ የተላቆጠ አፈር)
ተዥጎርጉሯል፥ ጴሮው (መሃል አናቱ ላይ ባለው ጌጥ) ላይ የተሰካው
የቀጭኔ ላባ በንፋስ ይርገበገባል ... እሱ ግን ፊቱን ዞሮ በርኮታው
ላይ ቁጭ ብሎ ጥርሱን በልምጭ ይፍቃል"
አንቺ ንብ አደለሽ
ምነው ቀፎሽን ዘጋግተሽ መቀመጥሽ
"ደልቲ ንፋሱ: ልጆችም
እንዳያስቸግሩኝ አለችው
ፈገግ ብላ እያየችው" እሱ ግን መልሷ አልተዋጠለትም ይህች ሰው! ነፋስና ልጅ የምትጠላ ምን ልትወድ ነው እህ! ብሎ ቆሽቱ
እያረረ ሃሣቡን ሳይናገር ከታጠቀው ዝናር አንድ ቀላህ አውጥቶ
ውታፏን ከፈተና በአውራ ጣቱ ጀርባ የትንባሆ ዱቄት ፈሰስ አድርጎ ጎንበስ ብሎ በአፍንጫው ቀዳዶች ሞዠቅ ሞዠቅ አድርጎ ሽቅብ ማገና በዐይኖቹ እንባ ፍጭጭ ብሎ ደጋግሞ ካስነጠሰው በኋላ
ትንባሆውን ለካርለት አቀበላት በሐመር ሴት ልጅ ትንባሆ መሳቧ ነውር የለውም! በፍቅረኞች መካከል ትንባሆ (ሱረት) መሰጣጣት ደግሞ አንዱ የመግባባታቸው ምልክት ነው።
"ሽማግሎች ለዛሬ ከብት ውጋ ብለውኝ ይኸው በሬዬን ይዠ መጣሁ" አላት ካርለት ትንባሆው ካስነጠሳት በኋላ ምክንያቱን የሰማች ቢሆንም ከእሱ አንደበት ለመስማት ብላ።
"ምነው ምናጠፋህ?" ስትለው መፋቂያውን አኘክ አኘክ አድርጎ ተፋና ረጋ ብሎ፣
"አንች ሰው ምነው ሥርዓት ቢኖርሽ ሴት በየት አገር ነው
የወንድን ጥፋት የምትጠይቀው?" አላት ደልቲ ካርለት እንዲህ
ስታጠፋ ጎንበስ ብላ እግሯን
እንድትይዝ አድርጎ ጡቷን
እንዳይመታ እየተጠነቀቀ ሁለት ሶስት ቀን በባራዛ አርጩሜ ደህና አድርጎ እየገረፈ ቢገራት ልክ እንደ ስልጡን አህያ ትሰግር እንደነበር አስታውሶ እህ! ሽማግሎች እንዳሉትስ በመታረሚያዋ ጊዜ
ስታጠፉ እኔ እንጂ ሌላ ማን ይታዘንበታል! ብሎ አዝኖ ጢቅ አድርጎ ምራቁን ተፋና ጥርሱን ይፍቅ ገባ።
"ጎይቲ ስታለቅስ ነው የምትውል አይተሃት ታውቃለህ?"አለችው ካርለት በጥያቄዋ ጎርጉራ አንድ አዲስ ነገር ባገኝ ብላ።
"ሰማሁ! እኔን እህቴን ምን የከፋ ችግር መጣባት! አዘነ
ደልቲ።
"ለዚህ ምን መፍትሔ አለው ታዲያ?" ስትል ካርለት ደልቲ
ሰረቅ አድርጎ አይቷት
"ምን መፍትሄ ይኖረዋል ሽማግሌ ያለውን መቀበል ነው እንጂ።
"ጎይቲ ከከሎ ጋር ከተጋቡ ወዲህ እኮ ሌላ ወንድ አታውቅም "እንደገና ለዓመል ያህል ሰረቅ አድርጎ እንደዘበት አያት የለበሰችው
ቆዳ የፊተኛው ክፍል ጉያዋ ውስጥ ተሸጉጦ: የቀኝ ጭኗ ውስጥ ክፍል እንደ ጥጥ ንጥት ብሎ ታየው"
"ተታናናሽ ወንድሞቹ ጋርስ አልቀበጠችም?"
"ከሎ ታናሽ ወንድም እኮ የለውም ሁሉም የእሱ ታላላቆች ናቸው"" ስትለው ታናሽ ወንድም እንደሌለው እያወቀ የረሳበት ምክንያት እየገረመው
"ተዘመዱ ወንዶችስ ጋር?" ካርለት የሰጎን ላባ የሰካበት ጴሮ የተተለተለውን ሳንቃ ደረቱን እንደ አቦ ሸማኔ ቀጠን ያለ ወገቡን አይታ ምራቋን ከምላሷ ስር መጣ ዋጠችና,
"ከማንም ጋር አልቀበጠችም ካለ ከሎ በቀር" አለችው
"እህ!" ሲል ካርለት ቀጥሎ የሚለውን ለመስማት ጆሮዋን መዘዘች እሱ ግን ጭራሽ ያልጠበቀችውን ጥያቄ
"የምጠጣው ውሃ ትሰጭኝ?" አለ ከኮዳዋ በኩባያ ቀድታ ውሃ
ስትሰጠው ቀና ብሎ አይቷት
"እሱን አንች ጠጭው፤ ለኔ በሾርቃ ስጭኝ" አላት ካርለት ውሃ ለማምጣት ሄደች ደልቲ አረማመዷን÷ ዳሌዋን ወገቧን ከኋላዋ የሚወናወነውን ቆዳዋን ጥርሱን እየፋቀ አየና ምራቁን ጢቅ አድርጎ ተፋና የበረቱ ከብቶች ቀለማቸው የተለያዬ ነው ቀይ፥
ዳልቻ: ነብርማ: ነጭ የካርለትም ቀለሟ ነጭ መሆኑ ሚስቶቹን
እንደ ከብቶቹ ቀለም ማሳመሩን ሲያስብ የደስታ ስሜት ተሰማው መልሶ ደግሞ የሐመር ልጃገረዶች እንዳለቁ ሁሉ ከዚች አግድም አደግ ጋር ቢቀርብኝስ ብሎ አሰበ አንዴ ግን አገባሻለሁ ብሏል1
ስለዚህ ቃሉን ማጠፍ አልፈለገም ግዴለም አገባታለሁ ድምጿ ግን
ምነው ተዛሬ ነገ ቃናው አይጣፍጥ? ብልግናዋና ድምጿ እንጂ ሴትነቷስ እያለ ሲያስብ ካርለት ውሃ በሾርቃ ይዛለት ብቅ አለች
ከርቀት እያያት ደሞ ደህና ገብሮ የነበረው ሰውነቷ እንደ ምስጥ ንጉስ ተመልሶ ለሰለሰ እያለ ሲያስብ ካርለት ሰው ጠርቷት
ዘወር ስትል የጀርባዋ ሰንበር ታየው ከሎ ከብት ሲዘል የተገረፈችው"
ደልቲ ትንሽ ፈርጠም ብሎ ሳቅ አለ ካርለት
አላየችውም ትዝ አለው ስትገረፍ ሰውነቷ የተንቀጠቀጠው ወድቃ
የተዘረረችው
ባለጌ! ብሎ ተቆጨና መልሶ ደግሞ አዘነላት ጀርባዋ ላይ
ያሉት የግርፊያ ሰንበሮች ጥቂት ናቸው ለሐመር ልጃገረድ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበር ሌላው ውበቷ ሲሆን ዳንስ ቦታና ጫካ ውስጥ ወንዱ
እንደ አኮርዲዎን መጫወቻ ሰንበሮቹን በጣቱ እየነካካ የፍቅረኛውን የፍቅር ቅላፄ በማስተካከል የጋራ የፍቅር ስሜት የሚፈጥሩበት ነው
ሴቷና ወንዱ
በልጃገረድ ጀርባ ላይ ባለ የግርፊያ ሰንበር ላይ ሻካራ የእጅ ጣት ጫፎችን ማንቀሳቀስ ትናጋው በፍቅረኛው ምላስ የተነካ ያህል በስሜት ንዝረት መላ ሰውነቱ ያረግዳል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበሯ ጀርባዋ ላይ የበዛ ዘመደ ብዙ' ካነሰ ደግሞ ዘመደ ትንሽ ናት ይባላል ብዙ ጊዜ ልጃገረዶች እርስ በርስ
ስለዚህ ሲጨዋወቱ
ይእ! ይሄ ሁሉ ማን ሲዘል የተገረፍሽው ነው? ተብላ
የተጠየቀች እንደሆነ እጅዋን አዙራ ጀርባዋን እየዳሰሰች
ይእ! ይሄ የባልዳምቤ
ይሄ የሸረምቤ ይሄ የላሎምቤ …እያለች ትዘረዝራለች ልጃገረዷ በእነዚህ ሁሉ ዘመዶችዋ ስትፎክርና ሳትፈራ ስትገረፍ ያያት ደግሞ ስንትና ስንቱ ወንድ ተመኝቷታል ከስንቱ ጋርስ ቀብጣለች ሊያገባት የፈለገውስ እንዴት እንደሚበዛ መገመቱ አይቸግርም አንድ
የሐመር ወንድ ደግሞ ሌላው የተመኛትን ያፈቀራትን የራሱ አድርጎ ከማግባት የበለጠ ትልቅ
ክብር የለም በሐመር የጋብቻ አለም።
ካርለት ግን የተገረፈችው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፤ የዛን ቀንም ግረፉኝ ብላ አልፎከረችም ስትገረፍም ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ
ስታለቅስ በመጨረሻም ህሊናዋን ስታ ስትወድቅ ምድረ ጎረምሳ ተሳስቆባታል እንጂ ማንም ለፍቅር አልተመኛትም ደልቲ ይህን
አስታውሶ
ወዲህ ወዲያ ስትል እንደ ፍየል ጅራት ስትወናወን እንጂ እሷስ ብትሆን ስንትና ስንት ዘመዶችዋ ከብት ሲዘሉ ብትኖር ኖሮ
የመገረፉ እድል መች ያመልጣት ነበር! እያለ ሲትከነከን ካርለት
አጠገቡ ደርሳ ውሃ የያዘ ሾርቃውን አቀበለችው
እየተጉመጠመጠ ደጋግሞ ተፋና ስምጥጥ አድርጎ ጠጥቶ ባይሮ ኢሜ ብሎ
አመሰገናት እግዜር ይስጥልኝ ለማለት
ካርለት ሾርቃውን
ሾርቃውን ልትመልስ ሄደች ያን ጊዜ ደልቲ ደሙ ፈላ ነደደው ተቀብላ ፈንጠቅ አድርጋ ደፋችውና
ይህች አሳሳች! ብሎ እራሱን ለማረጋጋት እየሞከረ ከመቀመጫው ተነሳ
"ይእ! እህ የታል አያ ደልቲ? አለ አሁን ውሃ ብሎኝ
ሰጥቸው መጣሁ አላልሽኝ?" አለች ጎይቲ ከካርለት ጋር ወደ ድንኳኗ
እየተጠጉ
"ጎይቲ አሁን እኮ እዚህ ቁጭ ብሎ ስናወራ ቆይተን ውሃ ስጭኝ ብሎኝ ሰጥቸው ሾርቃውን መልሼ: አንችን ጠርቸሽ መጣን በዚህ ቅፅበት የት ሄደ?"
"ይእ! እኔን ትጠይቂያለሽ ደሞ ይልቅ አንች ምንሽ ውስጥ ከተትሽው? አያ ደልቲ መቼም ካለ ነገር እንዲህ ሹልክ ብሎ እንደ
ሌባ አይጠፋም ተቀያየማችሁ?"
"ኧረ በጭራሽ"
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ካርለት ድንኳናን ዘግታ ስትፅፍ የሰው ኮቴ የሰማች መሰላትና ጆሮዋን አቁማ አዳመጠች
"ካርለት?"
"የስ" ብላ ቶሎ በማስተካከል "ዬ! አለች - እንደ ሐመር ልጃገረዶችı ካርለት የጠራት ሰው ማን እንደሆነ አውቃዋለች
ደልቲ ነው ቀብራራው ጀግና የድንኳኗን ዚፕ ከፍታ ፈገግ ብላ አየችው" ሰውነቱ በአኖ (ከኦሞ ወንዝ ዳር በመጣ የተላቆጠ አፈር)
ተዥጎርጉሯል፥ ጴሮው (መሃል አናቱ ላይ ባለው ጌጥ) ላይ የተሰካው
የቀጭኔ ላባ በንፋስ ይርገበገባል ... እሱ ግን ፊቱን ዞሮ በርኮታው
ላይ ቁጭ ብሎ ጥርሱን በልምጭ ይፍቃል"
አንቺ ንብ አደለሽ
ምነው ቀፎሽን ዘጋግተሽ መቀመጥሽ
"ደልቲ ንፋሱ: ልጆችም
እንዳያስቸግሩኝ አለችው
ፈገግ ብላ እያየችው" እሱ ግን መልሷ አልተዋጠለትም ይህች ሰው! ነፋስና ልጅ የምትጠላ ምን ልትወድ ነው እህ! ብሎ ቆሽቱ
እያረረ ሃሣቡን ሳይናገር ከታጠቀው ዝናር አንድ ቀላህ አውጥቶ
ውታፏን ከፈተና በአውራ ጣቱ ጀርባ የትንባሆ ዱቄት ፈሰስ አድርጎ ጎንበስ ብሎ በአፍንጫው ቀዳዶች ሞዠቅ ሞዠቅ አድርጎ ሽቅብ ማገና በዐይኖቹ እንባ ፍጭጭ ብሎ ደጋግሞ ካስነጠሰው በኋላ
ትንባሆውን ለካርለት አቀበላት በሐመር ሴት ልጅ ትንባሆ መሳቧ ነውር የለውም! በፍቅረኞች መካከል ትንባሆ (ሱረት) መሰጣጣት ደግሞ አንዱ የመግባባታቸው ምልክት ነው።
"ሽማግሎች ለዛሬ ከብት ውጋ ብለውኝ ይኸው በሬዬን ይዠ መጣሁ" አላት ካርለት ትንባሆው ካስነጠሳት በኋላ ምክንያቱን የሰማች ቢሆንም ከእሱ አንደበት ለመስማት ብላ።
"ምነው ምናጠፋህ?" ስትለው መፋቂያውን አኘክ አኘክ አድርጎ ተፋና ረጋ ብሎ፣
"አንች ሰው ምነው ሥርዓት ቢኖርሽ ሴት በየት አገር ነው
የወንድን ጥፋት የምትጠይቀው?" አላት ደልቲ ካርለት እንዲህ
ስታጠፋ ጎንበስ ብላ እግሯን
እንድትይዝ አድርጎ ጡቷን
እንዳይመታ እየተጠነቀቀ ሁለት ሶስት ቀን በባራዛ አርጩሜ ደህና አድርጎ እየገረፈ ቢገራት ልክ እንደ ስልጡን አህያ ትሰግር እንደነበር አስታውሶ እህ! ሽማግሎች እንዳሉትስ በመታረሚያዋ ጊዜ
ስታጠፉ እኔ እንጂ ሌላ ማን ይታዘንበታል! ብሎ አዝኖ ጢቅ አድርጎ ምራቁን ተፋና ጥርሱን ይፍቅ ገባ።
"ጎይቲ ስታለቅስ ነው የምትውል አይተሃት ታውቃለህ?"አለችው ካርለት በጥያቄዋ ጎርጉራ አንድ አዲስ ነገር ባገኝ ብላ።
"ሰማሁ! እኔን እህቴን ምን የከፋ ችግር መጣባት! አዘነ
ደልቲ።
"ለዚህ ምን መፍትሔ አለው ታዲያ?" ስትል ካርለት ደልቲ
ሰረቅ አድርጎ አይቷት
"ምን መፍትሄ ይኖረዋል ሽማግሌ ያለውን መቀበል ነው እንጂ።
"ጎይቲ ከከሎ ጋር ከተጋቡ ወዲህ እኮ ሌላ ወንድ አታውቅም "እንደገና ለዓመል ያህል ሰረቅ አድርጎ እንደዘበት አያት የለበሰችው
ቆዳ የፊተኛው ክፍል ጉያዋ ውስጥ ተሸጉጦ: የቀኝ ጭኗ ውስጥ ክፍል እንደ ጥጥ ንጥት ብሎ ታየው"
"ተታናናሽ ወንድሞቹ ጋርስ አልቀበጠችም?"
"ከሎ ታናሽ ወንድም እኮ የለውም ሁሉም የእሱ ታላላቆች ናቸው"" ስትለው ታናሽ ወንድም እንደሌለው እያወቀ የረሳበት ምክንያት እየገረመው
"ተዘመዱ ወንዶችስ ጋር?" ካርለት የሰጎን ላባ የሰካበት ጴሮ የተተለተለውን ሳንቃ ደረቱን እንደ አቦ ሸማኔ ቀጠን ያለ ወገቡን አይታ ምራቋን ከምላሷ ስር መጣ ዋጠችና,
"ከማንም ጋር አልቀበጠችም ካለ ከሎ በቀር" አለችው
"እህ!" ሲል ካርለት ቀጥሎ የሚለውን ለመስማት ጆሮዋን መዘዘች እሱ ግን ጭራሽ ያልጠበቀችውን ጥያቄ
"የምጠጣው ውሃ ትሰጭኝ?" አለ ከኮዳዋ በኩባያ ቀድታ ውሃ
ስትሰጠው ቀና ብሎ አይቷት
"እሱን አንች ጠጭው፤ ለኔ በሾርቃ ስጭኝ" አላት ካርለት ውሃ ለማምጣት ሄደች ደልቲ አረማመዷን÷ ዳሌዋን ወገቧን ከኋላዋ የሚወናወነውን ቆዳዋን ጥርሱን እየፋቀ አየና ምራቁን ጢቅ አድርጎ ተፋና የበረቱ ከብቶች ቀለማቸው የተለያዬ ነው ቀይ፥
ዳልቻ: ነብርማ: ነጭ የካርለትም ቀለሟ ነጭ መሆኑ ሚስቶቹን
እንደ ከብቶቹ ቀለም ማሳመሩን ሲያስብ የደስታ ስሜት ተሰማው መልሶ ደግሞ የሐመር ልጃገረዶች እንዳለቁ ሁሉ ከዚች አግድም አደግ ጋር ቢቀርብኝስ ብሎ አሰበ አንዴ ግን አገባሻለሁ ብሏል1
ስለዚህ ቃሉን ማጠፍ አልፈለገም ግዴለም አገባታለሁ ድምጿ ግን
ምነው ተዛሬ ነገ ቃናው አይጣፍጥ? ብልግናዋና ድምጿ እንጂ ሴትነቷስ እያለ ሲያስብ ካርለት ውሃ በሾርቃ ይዛለት ብቅ አለች
ከርቀት እያያት ደሞ ደህና ገብሮ የነበረው ሰውነቷ እንደ ምስጥ ንጉስ ተመልሶ ለሰለሰ እያለ ሲያስብ ካርለት ሰው ጠርቷት
ዘወር ስትል የጀርባዋ ሰንበር ታየው ከሎ ከብት ሲዘል የተገረፈችው"
ደልቲ ትንሽ ፈርጠም ብሎ ሳቅ አለ ካርለት
አላየችውም ትዝ አለው ስትገረፍ ሰውነቷ የተንቀጠቀጠው ወድቃ
የተዘረረችው
ባለጌ! ብሎ ተቆጨና መልሶ ደግሞ አዘነላት ጀርባዋ ላይ
ያሉት የግርፊያ ሰንበሮች ጥቂት ናቸው ለሐመር ልጃገረድ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበር ሌላው ውበቷ ሲሆን ዳንስ ቦታና ጫካ ውስጥ ወንዱ
እንደ አኮርዲዎን መጫወቻ ሰንበሮቹን በጣቱ እየነካካ የፍቅረኛውን የፍቅር ቅላፄ በማስተካከል የጋራ የፍቅር ስሜት የሚፈጥሩበት ነው
ሴቷና ወንዱ
በልጃገረድ ጀርባ ላይ ባለ የግርፊያ ሰንበር ላይ ሻካራ የእጅ ጣት ጫፎችን ማንቀሳቀስ ትናጋው በፍቅረኛው ምላስ የተነካ ያህል በስሜት ንዝረት መላ ሰውነቱ ያረግዳል ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ
የግርፊያ ሰንበሯ ጀርባዋ ላይ የበዛ ዘመደ ብዙ' ካነሰ ደግሞ ዘመደ ትንሽ ናት ይባላል ብዙ ጊዜ ልጃገረዶች እርስ በርስ
ስለዚህ ሲጨዋወቱ
ይእ! ይሄ ሁሉ ማን ሲዘል የተገረፍሽው ነው? ተብላ
የተጠየቀች እንደሆነ እጅዋን አዙራ ጀርባዋን እየዳሰሰች
ይእ! ይሄ የባልዳምቤ
ይሄ የሸረምቤ ይሄ የላሎምቤ …እያለች ትዘረዝራለች ልጃገረዷ በእነዚህ ሁሉ ዘመዶችዋ ስትፎክርና ሳትፈራ ስትገረፍ ያያት ደግሞ ስንትና ስንቱ ወንድ ተመኝቷታል ከስንቱ ጋርስ ቀብጣለች ሊያገባት የፈለገውስ እንዴት እንደሚበዛ መገመቱ አይቸግርም አንድ
የሐመር ወንድ ደግሞ ሌላው የተመኛትን ያፈቀራትን የራሱ አድርጎ ከማግባት የበለጠ ትልቅ
ክብር የለም በሐመር የጋብቻ አለም።
ካርለት ግን የተገረፈችው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፤ የዛን ቀንም ግረፉኝ ብላ አልፎከረችም ስትገረፍም ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ
ስታለቅስ በመጨረሻም ህሊናዋን ስታ ስትወድቅ ምድረ ጎረምሳ ተሳስቆባታል እንጂ ማንም ለፍቅር አልተመኛትም ደልቲ ይህን
አስታውሶ
ወዲህ ወዲያ ስትል እንደ ፍየል ጅራት ስትወናወን እንጂ እሷስ ብትሆን ስንትና ስንት ዘመዶችዋ ከብት ሲዘሉ ብትኖር ኖሮ
የመገረፉ እድል መች ያመልጣት ነበር! እያለ ሲትከነከን ካርለት
አጠገቡ ደርሳ ውሃ የያዘ ሾርቃውን አቀበለችው
እየተጉመጠመጠ ደጋግሞ ተፋና ስምጥጥ አድርጎ ጠጥቶ ባይሮ ኢሜ ብሎ
አመሰገናት እግዜር ይስጥልኝ ለማለት
ካርለት ሾርቃውን
ሾርቃውን ልትመልስ ሄደች ያን ጊዜ ደልቲ ደሙ ፈላ ነደደው ተቀብላ ፈንጠቅ አድርጋ ደፋችውና
ይህች አሳሳች! ብሎ እራሱን ለማረጋጋት እየሞከረ ከመቀመጫው ተነሳ
"ይእ! እህ የታል አያ ደልቲ? አለ አሁን ውሃ ብሎኝ
ሰጥቸው መጣሁ አላልሽኝ?" አለች ጎይቲ ከካርለት ጋር ወደ ድንኳኗ
እየተጠጉ
"ጎይቲ አሁን እኮ እዚህ ቁጭ ብሎ ስናወራ ቆይተን ውሃ ስጭኝ ብሎኝ ሰጥቸው ሾርቃውን መልሼ: አንችን ጠርቸሽ መጣን በዚህ ቅፅበት የት ሄደ?"
"ይእ! እኔን ትጠይቂያለሽ ደሞ ይልቅ አንች ምንሽ ውስጥ ከተትሽው? አያ ደልቲ መቼም ካለ ነገር እንዲህ ሹልክ ብሎ እንደ
ሌባ አይጠፋም ተቀያየማችሁ?"
"ኧረ በጭራሽ"
👍27❤2
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
ጎይቲና ካርለት እንጨታቸውን ለቃቅመው አስረው፤ ዛፍ ስር
ተቀምጠዋል ነፋሻ ነው ቀኑ ፀሐይዋን ግን ባዘቶ ዳመና እየሸፈናት ሽቅብ ወደ ቡስካ ተራራ ያቀናል" እፅዋቱ ይወዛወዛሉ ወፎች ያዜማሉ ጎይቲም ታዜማለች ... ካርለት ደግሞ ህብረ ዝማሬውን ህሊናዋን ከፍታ ትቀዳዋለች
"ይእ ዛሬ ማታ ትልቅ ፌስታ እኮ ነው"
"ለምን?"
"አያ ደልቲ ከብት ይወጋላ! ከዚያ እየተበላ: ሸፈሮ ቡና
እየተጠጣ ይቆይና ማታ ሰማዩ ላይ በምትዋኘው ጨረቃ ልብሽ ስውር
ብሎ ጫካ እስኪገባ መጫወት ነው! ብላ ጎይቲ ከተቀመጠችበት ተነስታ እያቀነቀነች ዳሌዋን በማዞር መደነስ ጀመረች ጎይቲ ልቧ በሃዘን የተሰበረ ቢሆንም እራሷን ለማስደሰት
የምታደርገውን ጥረት ካርለት ስታይ አይ የሰው ልጅ ለምን ይሆን
ከደስታ ጊዜ ይልቅ በመከራው ጊዜ መዝፈን የሚወድ? ብላ ስታስብ
"ይእ ቁጭ ብለሽ
ታያለሽ?" ጎይቲ ካርለትን ሳቅ ብላ "ጠየቀቻት
ካርለቴ!- ልጃገረድ
ዳንስ አይታ አስችሏት ተመልካች ትሆናለች ቢባል ማን ያምናል!"
ጎይቲ እንደ ወንዶች እየሰገረች በማቀንቀን ካርለትን እንደ ልጃገረድ ደንሽ አለቻት ተነሳች ካርለት እየተሳሳቁ እንደ ወንድና
ልጃገረድ እየሆኑ ሲደንሱ ቆዩና ሮጠው ከስኬ አሸዋ ሄዱ እዚያም
ዘፈኑን አስነኩት ከዚያ ጭሮሽ ውሃው ጎን ጎይቲ የተፈጨውን የካሮ አፈር አውጥታ በጥብጣ ካርለትን
"ይእ! ነይ ልቀባሽ?" አለቻት
"ልቀባ ብለሽ ነው ጎይቲ?"
ታሾፊያለሽ ይሆን? ዛሬማ መቅበጥሽ የት ይቀራል!"
"ከማን ጋር ጎይቲ?"
"ይእ ተአንበሳሽ ነዋ!"
"እሱማ ተቀይሞኝ ሄዷል ..."
"ይእ! አያ ደልቲ እንዳስቀየምሽው እንደናሱ
(የጎሳው አባል ብትሆኝ ኖሮ ይመታሽ ነበር አንች ግን ፀንጋዛ (ባዕድ) ነሽ
ከብት ዝላይ ላይ ወይም ታገባሽ በኋላ ካልሆነ ዝንብሽንም እሽ ማለት ስለማይችል ራቅ ብሎ ብስጭቱን ሊያቀዘቅዝ ነው የሄደ‥
የሐመር ወንድ ሲቀየም እንደ አንበሳ ነው ጎምለል ብሎ ጫካ ይገባል እንጂ እንደ ሴት ቃል መለዋወጥ አይወድም ወይ ይማታና
ካለበለዚያም ከአጠገብሽ ይሄድና በኋላ ሁሉንም ረስቶ ይመጣል ወንድ ቂም ሲይዝ ነውር ነው!''
"እኔና ደልቲም ዛሬውኑ እንታረቃለን በይኛ?"
ይእ! እየነገርሁሽ የሐመር ወንዶችን ባህሪ ልቅም አድርጌ ነው የማውቀው" በረቱ በከብት የሞላ የአባቱን ጠላት የገደለ
የሐመር ወንድ ልቡ እንደ ክረምት ወንዝ ሞልቶ የተንቸረፈፈ ነው አያ ደልቲ እንዲያ ስለሆነ ነው ሲንጎማለል ሲያገሳ ሲጨብጥ ልቡ እንደ አዙሪት አሽከርክሮ ሳንቃ ደረቱ ላይ የሚጥል" አለቻት
"ዛሬ እድለኛ ነኛ! ካርለት ሳቅ ብላ ጎይቲን አየቻት
"ይእ! ዛሬማ የልብሽ መቦረቂያ ቀን ናት አያ ደልቲ ያን ሁሉ ጎጆ አልፎ አንች ዘንድ ለምን መጣ?ውሃ አምጭልኝስ ብሎ
ለምን ላከሽ ሞኝት! ተኝቶ አልሞሻል ማለት ነው ተዚያ ህልሙን ሊያይ መጣ አየሽ ስትንቀሳቀሽ ደግሞ ዳሌሽን ማዬት ፈልጎ ውሃ አምጭልኝ ብሎ ላከሽ ህልሙ እውን መሆኑን አረጋግጦ
በዐይኖቹ የሚያረግደውን ሰውነትሽን ጎረሰው ያን ጉርሻውን ማታ ጫካ መካከል ወስዶሽ እስቲውጠው ሲያመነዥከው ያመሻል ዛሬ ማታ በጨረቃ ድባብ የአያ ደልቲ የጥም መቁረጫ አንች ነሽ!" ጎይቲ
በተናገረች ቁጥር ልቧ ቅልጥ ብላ የፈሰሰች ያክል ሰውነቷ ዛለ ዐይኖችዋ ተስለመለሙ ካርለትም ጎይቲ በተናገረችው ጎመጀች ጮማ እንደሚያኝክ ሰው አፏ ደስ በሚል ፈሳሽ ተሞላ
"ጎይቲ ዛሬ አንች ለምን ከእሱ ጋር አትቀብጭም?"
"ይእ! እንዲያ በይኝ!" ብላ ጎይቲ እያጨበጨበች ሳቀችና
"ምነው ካርለቴ ይኸማ ነውር ነው!" ብላ ኮስተር አለች
ካርለት ኮስተር ብላ ስታያት ስሜቷ ተምታታባት ኦ!
አምላኬ አጠፋሁ ይሆን! ጎይቲ ያለችው ከሐመር ማህበራዊ ህይወት
ጫፍ ላይ ነው ካላረገዘች
ተደግፋ ወደማትነሳበት
ገደል ትወድቃለች ስለዚህ
ምን አልባት የመውለድ ችግሩ የከሎ ከሆነ ብላ አስባ
"ጎይቲ ምን ችግር አለው - እስቲ ማህፀንሽንም ፈትሽው”?"
ካርለቴ በሆነማ በማን እድሌ የአባቴ ደንብ ግን አይፈቅድም" ብላ ትክዝ አለችና" ከሎ ስንቱን የለመድሁትን ህይወት ነስቶኛል የእኔ በደል ግን የከፋ ነው ልጅ ወልዶ እንዳይስም በልጅነቱ የተሰበረው ልቡ እንዳይጠገን አደረኩት ያ
በደሌ አንሶኝ ደሞ ከደሙ ውጭ ልክዳው! የአባቴን ደንብ ከምሽር: የእሱን እምነት ከማጣ አሁኑኑ ጦሽ ብዬ እንደ ወፍ እንቁላል ለምን አልፈርጥም አለች
ካርለት የምትናገረው ጠፋት ጓደኛዋ: አዛኝዋ መካሪዋ ጎይቲ አንተነህ ፅልመት ሊውጣት እየገሰገሰ ገው እሷ ደግሞ
በጓደኝነቷ ወደ ብርሃኑ ስባ ልታስቀራት ትፈልጋለች ከእሷ ጉተታ ጎን ባህልና ደንብ ፅልመቱ ውስጥ ሆኖ ጠምጥሞ አስሮ ወደ እሱ
እየሳባት ነው" ጎይቲ ህይወቷ በጨለማ አይዋጥም ባለኝ አቅም
ሊጥላት ከሚስባት ጋር እሳሳባለሁ ... እያለች ካርለት ስታስብ
"ካርለቴ ዙሪ ላሸክምሽ?" ብላ ጎይቲ እንጨቱን አሸክማት የራሷንም ተረዳድተው ተሸክማ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ጎይቲ
እያንጎራጎረች እየተሳሳቁ ከኋላ በጨሌ የተሽቆጠቆጠውን የፍዬል
ቆዳቸውን እያወናወኑ የማታ ጀምበር ሳትጠልቅ ለመድረስ ወደ መንደራቸው ሄዱ።
ካርለትና ጎይቲ መንደር ደርሰው ዕረፍት ከወሰዱ በኋላ ጎይቲ ካርለትን ጉያዋ አስገብታ ፀጉሯን በካሮ አፈር እንደገና እጣንና ቅቤ
አላቁጣ ስታለሳልስላት አንድ ጊዜ የሴት ጩኸት ሰሙና ተሯሩጠው
ሄዱ ጩኸቱን ወደሰሙበት አቅጣጫ ኮቶ ቀደም ብላ የአየችውን በምልክት እያሳየቻቸው አፏን በመተምተም ዝም በሉና ተደበቁ ብላ በጆሯቸው አንሾካሾከችላቸው"
ሸረንቤ ሚስቱን ጎንበስ አድርጎ እየገረፉት ነው ካርለት ያን ስታይ ስቅጥጥ አላት" ኮቶና ጎይቲ ግን አስቂኝ ትርኢት እንደሚያዩ
ሁሉ በሳቅ ይፍነከነካሉ
ጎይቲ ለምን ይመታታል?" ካርለት አካሏ በፍርሃት
እየተንገጫገጨ ጠየቀቻቸው"
"ይእ! ሚስቱ አይደለች,"
"ብትሆንስ? አለች ካርለት ዐይኗን በየተራ ወደሁለቱም
አቅጣጫ እያንከራተተች ኮቶና ጎይቲ በካርለት ጥያቄ ሳቁባት
ይእ! ሴት ስትገረፍ ጥሩ ነዋ!" አለች ኮቶ ፈገግ በማለት ወደ ካርለት ዞራ
"ለምን?" የካርለት የግንባር ቆዳ ተጨማደደ ፊቷ ጨው
እንደነሰነሱበት ሁሉ ነጣ
"ይእ! ደግማ አታጠፋማ ደሞ መመታት ፍቅር ነው ሴት ልጅ ባሏ ዘንድ ስትመጣ እንደ ዱባ ድፍንፍን ብላ ነው ድቡልቡሉን የሴትን ልጅ ልብና ጭን የሚበረግደው ግርፊያ ነው" ብላ ሳቀች ኮቶ
"አሁን እናንተ ስትመቱ ደስ ይላችኋል?"
"ይእ! ግርፊያ አይነት አይነት አለው በዓይነቱ ተሆነ:
ናፍቀሽ ከጠበቅሽው ደስ ይላል ለምን ደስ አይለን" አለች ኮቶ ጎይቲ ግን ዝም አለች
"አንችስ ጎይቲ?"
"እኔማ እድሜ ለእንዳንች አይነቱ ብመኝስ የታባቴን አገኘዋለሁ እንደምትታለብ ላም አንገቴን በዚ
ለስላሳ የህፃን እጁ ይሸኝ እንጂ እይ ይልቅ! ተመልከቱ የሚያረጋትን ..." አለች ጎይቲ ግርፊያውን በጉጉት እያየች
ሸሮምቤ ሚስቱ የሆነ ነገር ስትቀባጥር ከቆየች
ግርፊያውን አቁሞ ቀና በይ? አላት አርጩሜውን ወርውሮ በሾርቃ ከተቀመጠው ቅቤ በቀኝ እጁ ጣት ጠንቁሎ ጀርባዋን ቀባ ቀባ አደረገላት„ ሚስቱ ግን ቆጣ ቆጣ ትላለች እንባዋን እየጠረገች።
ካርለት ለተገረፈችው ሴት አዘነችላት በመጨረሻ ግን እጅዋን ጎትቶ ወደ ጎጆው ይዟት ገባ ጎይቲና ኮቶ ተያይተው ከልባቸው
ተሳሳቁ
"ምንድነው?" ካርለት የባሰ ግራ ተጋባች
"ይእ! ቆጣ ቆጣ ስትል አላየሻትም አሁን ትንሽ ቆይተሽ ብታያት ቁጣዋ በደስታ ተተክቶ ታገኛታለሽ "
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
ጎይቲና ካርለት እንጨታቸውን ለቃቅመው አስረው፤ ዛፍ ስር
ተቀምጠዋል ነፋሻ ነው ቀኑ ፀሐይዋን ግን ባዘቶ ዳመና እየሸፈናት ሽቅብ ወደ ቡስካ ተራራ ያቀናል" እፅዋቱ ይወዛወዛሉ ወፎች ያዜማሉ ጎይቲም ታዜማለች ... ካርለት ደግሞ ህብረ ዝማሬውን ህሊናዋን ከፍታ ትቀዳዋለች
"ይእ ዛሬ ማታ ትልቅ ፌስታ እኮ ነው"
"ለምን?"
"አያ ደልቲ ከብት ይወጋላ! ከዚያ እየተበላ: ሸፈሮ ቡና
እየተጠጣ ይቆይና ማታ ሰማዩ ላይ በምትዋኘው ጨረቃ ልብሽ ስውር
ብሎ ጫካ እስኪገባ መጫወት ነው! ብላ ጎይቲ ከተቀመጠችበት ተነስታ እያቀነቀነች ዳሌዋን በማዞር መደነስ ጀመረች ጎይቲ ልቧ በሃዘን የተሰበረ ቢሆንም እራሷን ለማስደሰት
የምታደርገውን ጥረት ካርለት ስታይ አይ የሰው ልጅ ለምን ይሆን
ከደስታ ጊዜ ይልቅ በመከራው ጊዜ መዝፈን የሚወድ? ብላ ስታስብ
"ይእ ቁጭ ብለሽ
ታያለሽ?" ጎይቲ ካርለትን ሳቅ ብላ "ጠየቀቻት
ካርለቴ!- ልጃገረድ
ዳንስ አይታ አስችሏት ተመልካች ትሆናለች ቢባል ማን ያምናል!"
ጎይቲ እንደ ወንዶች እየሰገረች በማቀንቀን ካርለትን እንደ ልጃገረድ ደንሽ አለቻት ተነሳች ካርለት እየተሳሳቁ እንደ ወንድና
ልጃገረድ እየሆኑ ሲደንሱ ቆዩና ሮጠው ከስኬ አሸዋ ሄዱ እዚያም
ዘፈኑን አስነኩት ከዚያ ጭሮሽ ውሃው ጎን ጎይቲ የተፈጨውን የካሮ አፈር አውጥታ በጥብጣ ካርለትን
"ይእ! ነይ ልቀባሽ?" አለቻት
"ልቀባ ብለሽ ነው ጎይቲ?"
ታሾፊያለሽ ይሆን? ዛሬማ መቅበጥሽ የት ይቀራል!"
"ከማን ጋር ጎይቲ?"
"ይእ ተአንበሳሽ ነዋ!"
"እሱማ ተቀይሞኝ ሄዷል ..."
"ይእ! አያ ደልቲ እንዳስቀየምሽው እንደናሱ
(የጎሳው አባል ብትሆኝ ኖሮ ይመታሽ ነበር አንች ግን ፀንጋዛ (ባዕድ) ነሽ
ከብት ዝላይ ላይ ወይም ታገባሽ በኋላ ካልሆነ ዝንብሽንም እሽ ማለት ስለማይችል ራቅ ብሎ ብስጭቱን ሊያቀዘቅዝ ነው የሄደ‥
የሐመር ወንድ ሲቀየም እንደ አንበሳ ነው ጎምለል ብሎ ጫካ ይገባል እንጂ እንደ ሴት ቃል መለዋወጥ አይወድም ወይ ይማታና
ካለበለዚያም ከአጠገብሽ ይሄድና በኋላ ሁሉንም ረስቶ ይመጣል ወንድ ቂም ሲይዝ ነውር ነው!''
"እኔና ደልቲም ዛሬውኑ እንታረቃለን በይኛ?"
ይእ! እየነገርሁሽ የሐመር ወንዶችን ባህሪ ልቅም አድርጌ ነው የማውቀው" በረቱ በከብት የሞላ የአባቱን ጠላት የገደለ
የሐመር ወንድ ልቡ እንደ ክረምት ወንዝ ሞልቶ የተንቸረፈፈ ነው አያ ደልቲ እንዲያ ስለሆነ ነው ሲንጎማለል ሲያገሳ ሲጨብጥ ልቡ እንደ አዙሪት አሽከርክሮ ሳንቃ ደረቱ ላይ የሚጥል" አለቻት
"ዛሬ እድለኛ ነኛ! ካርለት ሳቅ ብላ ጎይቲን አየቻት
"ይእ! ዛሬማ የልብሽ መቦረቂያ ቀን ናት አያ ደልቲ ያን ሁሉ ጎጆ አልፎ አንች ዘንድ ለምን መጣ?ውሃ አምጭልኝስ ብሎ
ለምን ላከሽ ሞኝት! ተኝቶ አልሞሻል ማለት ነው ተዚያ ህልሙን ሊያይ መጣ አየሽ ስትንቀሳቀሽ ደግሞ ዳሌሽን ማዬት ፈልጎ ውሃ አምጭልኝ ብሎ ላከሽ ህልሙ እውን መሆኑን አረጋግጦ
በዐይኖቹ የሚያረግደውን ሰውነትሽን ጎረሰው ያን ጉርሻውን ማታ ጫካ መካከል ወስዶሽ እስቲውጠው ሲያመነዥከው ያመሻል ዛሬ ማታ በጨረቃ ድባብ የአያ ደልቲ የጥም መቁረጫ አንች ነሽ!" ጎይቲ
በተናገረች ቁጥር ልቧ ቅልጥ ብላ የፈሰሰች ያክል ሰውነቷ ዛለ ዐይኖችዋ ተስለመለሙ ካርለትም ጎይቲ በተናገረችው ጎመጀች ጮማ እንደሚያኝክ ሰው አፏ ደስ በሚል ፈሳሽ ተሞላ
"ጎይቲ ዛሬ አንች ለምን ከእሱ ጋር አትቀብጭም?"
"ይእ! እንዲያ በይኝ!" ብላ ጎይቲ እያጨበጨበች ሳቀችና
"ምነው ካርለቴ ይኸማ ነውር ነው!" ብላ ኮስተር አለች
ካርለት ኮስተር ብላ ስታያት ስሜቷ ተምታታባት ኦ!
አምላኬ አጠፋሁ ይሆን! ጎይቲ ያለችው ከሐመር ማህበራዊ ህይወት
ጫፍ ላይ ነው ካላረገዘች
ተደግፋ ወደማትነሳበት
ገደል ትወድቃለች ስለዚህ
ምን አልባት የመውለድ ችግሩ የከሎ ከሆነ ብላ አስባ
"ጎይቲ ምን ችግር አለው - እስቲ ማህፀንሽንም ፈትሽው”?"
ካርለቴ በሆነማ በማን እድሌ የአባቴ ደንብ ግን አይፈቅድም" ብላ ትክዝ አለችና" ከሎ ስንቱን የለመድሁትን ህይወት ነስቶኛል የእኔ በደል ግን የከፋ ነው ልጅ ወልዶ እንዳይስም በልጅነቱ የተሰበረው ልቡ እንዳይጠገን አደረኩት ያ
በደሌ አንሶኝ ደሞ ከደሙ ውጭ ልክዳው! የአባቴን ደንብ ከምሽር: የእሱን እምነት ከማጣ አሁኑኑ ጦሽ ብዬ እንደ ወፍ እንቁላል ለምን አልፈርጥም አለች
ካርለት የምትናገረው ጠፋት ጓደኛዋ: አዛኝዋ መካሪዋ ጎይቲ አንተነህ ፅልመት ሊውጣት እየገሰገሰ ገው እሷ ደግሞ
በጓደኝነቷ ወደ ብርሃኑ ስባ ልታስቀራት ትፈልጋለች ከእሷ ጉተታ ጎን ባህልና ደንብ ፅልመቱ ውስጥ ሆኖ ጠምጥሞ አስሮ ወደ እሱ
እየሳባት ነው" ጎይቲ ህይወቷ በጨለማ አይዋጥም ባለኝ አቅም
ሊጥላት ከሚስባት ጋር እሳሳባለሁ ... እያለች ካርለት ስታስብ
"ካርለቴ ዙሪ ላሸክምሽ?" ብላ ጎይቲ እንጨቱን አሸክማት የራሷንም ተረዳድተው ተሸክማ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ጎይቲ
እያንጎራጎረች እየተሳሳቁ ከኋላ በጨሌ የተሽቆጠቆጠውን የፍዬል
ቆዳቸውን እያወናወኑ የማታ ጀምበር ሳትጠልቅ ለመድረስ ወደ መንደራቸው ሄዱ።
ካርለትና ጎይቲ መንደር ደርሰው ዕረፍት ከወሰዱ በኋላ ጎይቲ ካርለትን ጉያዋ አስገብታ ፀጉሯን በካሮ አፈር እንደገና እጣንና ቅቤ
አላቁጣ ስታለሳልስላት አንድ ጊዜ የሴት ጩኸት ሰሙና ተሯሩጠው
ሄዱ ጩኸቱን ወደሰሙበት አቅጣጫ ኮቶ ቀደም ብላ የአየችውን በምልክት እያሳየቻቸው አፏን በመተምተም ዝም በሉና ተደበቁ ብላ በጆሯቸው አንሾካሾከችላቸው"
ሸረንቤ ሚስቱን ጎንበስ አድርጎ እየገረፉት ነው ካርለት ያን ስታይ ስቅጥጥ አላት" ኮቶና ጎይቲ ግን አስቂኝ ትርኢት እንደሚያዩ
ሁሉ በሳቅ ይፍነከነካሉ
ጎይቲ ለምን ይመታታል?" ካርለት አካሏ በፍርሃት
እየተንገጫገጨ ጠየቀቻቸው"
"ይእ! ሚስቱ አይደለች,"
"ብትሆንስ? አለች ካርለት ዐይኗን በየተራ ወደሁለቱም
አቅጣጫ እያንከራተተች ኮቶና ጎይቲ በካርለት ጥያቄ ሳቁባት
ይእ! ሴት ስትገረፍ ጥሩ ነዋ!" አለች ኮቶ ፈገግ በማለት ወደ ካርለት ዞራ
"ለምን?" የካርለት የግንባር ቆዳ ተጨማደደ ፊቷ ጨው
እንደነሰነሱበት ሁሉ ነጣ
"ይእ! ደግማ አታጠፋማ ደሞ መመታት ፍቅር ነው ሴት ልጅ ባሏ ዘንድ ስትመጣ እንደ ዱባ ድፍንፍን ብላ ነው ድቡልቡሉን የሴትን ልጅ ልብና ጭን የሚበረግደው ግርፊያ ነው" ብላ ሳቀች ኮቶ
"አሁን እናንተ ስትመቱ ደስ ይላችኋል?"
"ይእ! ግርፊያ አይነት አይነት አለው በዓይነቱ ተሆነ:
ናፍቀሽ ከጠበቅሽው ደስ ይላል ለምን ደስ አይለን" አለች ኮቶ ጎይቲ ግን ዝም አለች
"አንችስ ጎይቲ?"
"እኔማ እድሜ ለእንዳንች አይነቱ ብመኝስ የታባቴን አገኘዋለሁ እንደምትታለብ ላም አንገቴን በዚ
ለስላሳ የህፃን እጁ ይሸኝ እንጂ እይ ይልቅ! ተመልከቱ የሚያረጋትን ..." አለች ጎይቲ ግርፊያውን በጉጉት እያየች
ሸሮምቤ ሚስቱ የሆነ ነገር ስትቀባጥር ከቆየች
ግርፊያውን አቁሞ ቀና በይ? አላት አርጩሜውን ወርውሮ በሾርቃ ከተቀመጠው ቅቤ በቀኝ እጁ ጣት ጠንቁሎ ጀርባዋን ቀባ ቀባ አደረገላት„ ሚስቱ ግን ቆጣ ቆጣ ትላለች እንባዋን እየጠረገች።
ካርለት ለተገረፈችው ሴት አዘነችላት በመጨረሻ ግን እጅዋን ጎትቶ ወደ ጎጆው ይዟት ገባ ጎይቲና ኮቶ ተያይተው ከልባቸው
ተሳሳቁ
"ምንድነው?" ካርለት የባሰ ግራ ተጋባች
"ይእ! ቆጣ ቆጣ ስትል አላየሻትም አሁን ትንሽ ቆይተሽ ብታያት ቁጣዋ በደስታ ተተክቶ ታገኛታለሽ "
👍25❤1🔥1
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
"ይእ!ጥሩ ነው እንጂ ካርለቴ ባልሽ በመታሽ ቁጥር የፍቅር ጥገትሽ ይጨምራል ለባልሽ የሚያስገሳውን ፍቅር ትሰጭዋለሽ እሱም እንደ ክረምት ዝናብ በፍቅሩ ያርስሻል ያን ጊዜ ይበልጥ
ትቀራረባላችሁ
በሐመር ሴት ሁለት ሶስት እስት ትወልድ ድረስ ባሏ
እንዲመታት ሰበብ ትፈጥራለች ልጃገረድ እያለሽ በኢቫንጋዲ
ላይ ዘመድሽ አብረሽኝ አልደነስሽም ብሎ ወይ ሌላ ምክንያት ፈጥሮ ይገርፍሻል" ዝምድናውን ለማጥበቅና አንድትግባቡ መፈለጉን ስለምታውቂ አትቀየሚውም ዘመድሽ ካልገረፈሽ ጠልቶሻል ወይንም ተቀይሞሻል ማለት ነው" ችግር ቢመጣ አይደርስልሽም
"ዘመድሽ ከብት ሲዘል እየፎከርሽ የምትገረፊውም የእሱን ዝምድና ለመግለፅ ሲሆን ያን አይቶ መከታሽ ይሆናል" ባልሽ ዘንድ
ስትሄጂም እንዲቀርብሽ:
ዘመድ እንዲሆንሽ
እንዲመታሽ ታደርጊያለሽ ያኔ ይመታሽ ይመታሽና
የኔ ሸጋ ... የኔ ወለላ
አርጊ ያልኸኝን ከአሁን ጀምሮ አንተን
አደርጋለሁ ስጭኝ ያልኸኝን እሰጥሃለሁ ማስደሰትና ልጅ መውለድ ይሆናል ስራዬ ስትይው እንደ ማሽላ
ዱቄት አፍሶ ደረቱ ላይ ነስንሶሽ ጫካ ውስጥ ይገባል አንች ደግሞ
እንደ አለቅት ደረቱን እየበሳሽ ሙቅ ልቡ ወስጥ ትገቢና ጎዝጉዘሽ
ትተኛለሽ ልቡ ውስጥ ሆነሽ ጡትሽን ሲዳስሰው ሁለመናሽን ሲያሸው
ለሴት ልጅ ከዚህ የበለጠ ምን ደስታና ጣእም ያለው ህይወት ይኖራታል!" አለች ጎይቲ ያቆመችውን ፀጉር መስራት ለመጀመር ካርለትን ወደ ጉያዋ ሳብ እያደረገቻት።
"ጎይቲ ታዲያ ዱላ ለሐመር ሴት የፍቅር መግለጫ ነው?"
"ይእ! ልጃገረድ ሆነሽ ዳንስ ቦታ የለመድሽው ፍቅር ባልሽ ዘንድ ስትሄጂም የሚጠብቅሽ ፍቅር ዱላ ነው"
"እናንተ አገር የፍቅር መግለጫችሁ ምንድን ነው?"
"መተሳሰብ: መሳሳም …"
"ይእ! ታለ ግርፊያ መተሳሰብ የተኮመታተረው ስሜትሽ ተመታቶ ሳይፍታታ መሳሳም በአፍንጫዬ ይውጣ! ምን ኑሮ ነው
እቴ!"
"ስላለመድሽው እንጂ …"
"ይእ! በይ ዝምበይ
እኔ የሌሎችን ነገርሁሽ እንጂ እኔማ ልምዴን ተገፍፌ እንደ ምትታለብ ላም ዳሌየንና ጡት ስሬን
የሚያሽ ባል አግብቻለሁ" እንዲያው ግን ካርለቴ ከሎ የልምዴን ሰጥቶኝ እንዲህ ማህፀኔ ቢደርቅ እኮ አይከፋኝም ነበር, ከዛሬ ነገ
ወንድ ወንድ ይሸተኛል ስል ከዛሬ ነገ የወንዶችን ለበቅ ያነሳል ስል ዕጣ ፋንታዬ እንዲህ ይክፋ ካርለቴ!" ብላ ምርር ብላ አዘነች
"አዝናለሁ ጎይቲ
ግርፊያ ለሐመር ልጃገረድ እንዲህ እንደ ውቅያኖስ ወለል የጠለቀ ትርጉም ያለው አይመስለኝም ነበር!
ስትላት ጎይቲ ውቅያኖስ ያለችው ባይገባትም
"ይእ! የአባት ደንብ አይደል ካርለቴ እናትሽ ባልሽ ዘንድ
ከመሄድሽ በፊት ባልሽ ሲመታሽ አታልቅሽ የባልሽ ጓደኞች ወደ ቤትሽ ሲመጡ ከጎሽ ቆዳ የተሰራ ጫማቸውን ጠመንጃቸውን ተቀብለሽ ተቀብለሽ ቤት አስገቢ ቀጥለሽ ከውጭ ቁርበት አንጥፈሽ ሸፈሮ ቡና አፍይላቸው" የባልሽን የአደን ጓደኛ ሚሶ'
የዝላይ ወቅት ጓደኛውን ባርግያ በይ በባራዛ አርጩሜ ገርፈው
ምን ተሰማሽ? ሲሉሽ ፈገግ ብለሽ ምንም በያቸው ያን ጊዜ በማርና ወተት ያደገች ተጨዋች ናት ብለው ይግባቡሻል" ለባልሽም
አንችን አሞጋግሰው ስለሚነግሩት ይቀርብሻል"
"ሲመቱሽ ካለቀስሽና አንገትሽን ከደፋሽ ግን ከብትና ፍየል አልጠበቀችም ቀፎ አልሰቀለችም ድሀ አደግ ጨዋታ የማታውቅ
እንደ አነር ቁጡና ክፉ ናት ብለው ይጠሉሻል" ያን ሲሰማ ደግሞ ባልሽም ይጠላሻል ይርቅሻል ውሎው ከሌላ ሴት ጋር ይሆናል እያሉ ዘመዶችሽ መክረውሽ አለት ድንጋይ ልብሽ ውስጥ ጨምረሽ
ጠንካራ እሆናለሁ ብለሽ ባልሽ ዘንድ ሄደሽ የጠበቅሽውን ሁሉ
ስታጭው ምነው አትራቢ ምነው አታዝኝ!" ብላ ጎይቲ እንባዋን ፀጥ ብሎ እንዲፈስ ከፈተችው
ካርለትም ዐይኖችዋ በእንባ እንዳቀረዘዙ ጎይቲን እያባበለች አንድ ቃል በህሊናዋ ብልጭ ብሎ ድርግም አለ ፈለገችው
ያን ቃል ፈረንሳዮች ፍላጀላሲዬን ይሉታል እንግሊዞች ደሞ
ፍላጄሌሽን ደስ አላት ህሊናዋ ከትውስታው ክፍል ጀባ ያላትን ቃል ወደ ኖረበት ተመልሶ ሳይገባ አፈፍ አድርጋ ስለያዘችው
ፍላጀላሲዬን ስርዓት ባለው ወይንም ሃይል በተሞላበት
መንገድ በሃይማኖት ተከታዮች የሚፈፀም ግርፊያ ነው" በብዙ
የሃይማኖት ተቋማት ፍላጀላሲዬን በመባል የሚታወቀው ግርፊያ
የርኩስ መንፈስ የማስወጫ ስልትና መፈወሻ ዘዴ ተደርጎ ይቆጠራል"በጥንት "ዘመን የሚኖሩ ብዙ ሰዎች በግርፊያ መሰቃየትን እንደ
አምልኮዋዊ ፀጋ ይቆጥሩት ነበር በነዚህ ህዝቦች እምነት መገረፍ ወይን በአካላዊ ጉዳት መሰቃየት ከሃጢያታቸው መንፃታቸውን፥ከመቅሰፍት
መዳናቸውን የሚያረጋግጡበት
ሆኖ ሲታመንበት ቆይቷል
በሰሜን አሜሪካ ህንዶች: በስፖርታዎችና በሮማውያን
ግርፊያ የአማልክትን ወይንም የቅድመ አያቶችን
ምስል ጭንብል
ባጠለቀ ገራፊ የሚፈፀም ነበር" ይህ ድርጊት በአስራ ሶስተኛው ክፍለ
ዘመን አጋማሽና በአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመንም ቀጥሎ እንደ ጀርመን: ሆላንድ በመሣሰሉት አገሮችም ተስፋፍቶ ቆይቷል በብዙ አገሮች በበዓላት ቀን ወንዶች ጀርባቸውንና ደረታቸውን በአለንጋ
ይገረፋሉ።
ይህ አምልኮዋዊ እምነት እ.ኤ.አ. በ1349 ዓ.ም እንደነበሩት ፓትሪያርክ ክሌመንት በመሳሰሉ የሃይማኖት አባቶች ከረር ያለ ተቃውሞ ግርፊያ እየቀነሰ ቢመጣም በአሁኑ ዘመንም በደቡብ
የአውሮፓ ሀገሮች በላቲን አሜሪካውያንና በመካከለኛውና ሩቅ
ምስራቅ አገሮች የተለመደ ነው ለምሳሌ በታይዋን የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በየአመቱ በስቅለት ቀን እንደ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ መገረፍ: መሰቃየት: እጅና እግርን በሚስማር መቸንከር
የእየሱስ ክርስቶስን ፍቅር እንደ ማግኘት ምድራዊ ሃጢያትን እንደ መቀነስና ለሰማያዊው ህይወት በክብር መዝገብ እንደመመዝገብ
ይቆጠራል
ከዚህ ውጭ ግን ዘመንሁ በሚለው ህብረተሰብ በሁለቱም ፆታ ግርፊያ በብዙ ግለሰቦች የወሲብ ስሜት መቀስቀሻ ወይንም የወሲብ ስሜት ማርኪያ ስልት እንደሆነና የገራፊ ልብሶችና የመግረፊያ
አለንጋዎች የሚሸጡባቸው የወሲብ ሱቆች
በርካታ እየሆኑ
መጥተዋል እኒህ ግርፊያን እንደ ወሲባዊ የችግር መፍትሔ የሚቆጥሩ
ሰዎችን የስነ አዕምሮ ጠቢባን የስነ-አዕምሮ
ችግር ያለባቸው እንደሆኑ በመቁጠር ብዙ መላ ምቶችን እየደረደሩ ቢሆንም
የመገረፍ ፍላጎት ወይንም ሱስ ግን አንድም የተፈጥሮ ባህሪ ውጤት ወይንም እምነት የፈጠረው ፍላጎት ስለመሆኑ አያጠራጥርም ብላ አሰበችና የሐመሩ ግርፊያም ባህላዊ እምነት የፈጠረው የህሊናና
የአካል ዝግጁነት ውጤት ነው ብላ ደመደመች።
እየጨለመ ሲመጣ የእሳቱ ወጋገን ይበልጥ እየጎላ እየጎላ መጣ ወጣቶች ለስነ-ስርዓቱ ከሰበሰቡት እንጨት በተጨማሪ ከጫካ
ግንዲላውን: ጭራሮውን እየተሸከሙ እያመጡ ይከምራሉ ጥቂት ጎረምሶች ደግሞ ለወጠሌ ጥብስ የሚሆነውን ችካል በጩቤያቸው ይጠርባሉ ሌሎች የእድሜ ጓደኛ ጎረምሶች ደግሞ ከሳቱ ርቀው ተሰብስበው ያወጋሉ፤ አንዳንዴም
በተቀቡት ዥንጉርጉር የአኖ ቀለም ከሹልሹላቸው
ለዳንሱ ዝግጅት
የሰጎን ላባ ሰክተው
ጨሌያቸውን አንገታቸው
ላይ ደርድረው ግንባራቸው ላይ የጨሌ ገመድ
ቋጥረው ዳንሱንና ድሪያውን ናፍቀው ውስጥ ለውስጥ ይቋምጣሉ አልደርስ ብሏቸው"
"ሚሶ!" አለ አንዱ
አለ አንዱ ከመሀላቸው የአደን ጓደኞቹን የሰአት ማሳለፍያ ጨዋታ ሊያወጋቸው።
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
"ይእ!ጥሩ ነው እንጂ ካርለቴ ባልሽ በመታሽ ቁጥር የፍቅር ጥገትሽ ይጨምራል ለባልሽ የሚያስገሳውን ፍቅር ትሰጭዋለሽ እሱም እንደ ክረምት ዝናብ በፍቅሩ ያርስሻል ያን ጊዜ ይበልጥ
ትቀራረባላችሁ
በሐመር ሴት ሁለት ሶስት እስት ትወልድ ድረስ ባሏ
እንዲመታት ሰበብ ትፈጥራለች ልጃገረድ እያለሽ በኢቫንጋዲ
ላይ ዘመድሽ አብረሽኝ አልደነስሽም ብሎ ወይ ሌላ ምክንያት ፈጥሮ ይገርፍሻል" ዝምድናውን ለማጥበቅና አንድትግባቡ መፈለጉን ስለምታውቂ አትቀየሚውም ዘመድሽ ካልገረፈሽ ጠልቶሻል ወይንም ተቀይሞሻል ማለት ነው" ችግር ቢመጣ አይደርስልሽም
"ዘመድሽ ከብት ሲዘል እየፎከርሽ የምትገረፊውም የእሱን ዝምድና ለመግለፅ ሲሆን ያን አይቶ መከታሽ ይሆናል" ባልሽ ዘንድ
ስትሄጂም እንዲቀርብሽ:
ዘመድ እንዲሆንሽ
እንዲመታሽ ታደርጊያለሽ ያኔ ይመታሽ ይመታሽና
የኔ ሸጋ ... የኔ ወለላ
አርጊ ያልኸኝን ከአሁን ጀምሮ አንተን
አደርጋለሁ ስጭኝ ያልኸኝን እሰጥሃለሁ ማስደሰትና ልጅ መውለድ ይሆናል ስራዬ ስትይው እንደ ማሽላ
ዱቄት አፍሶ ደረቱ ላይ ነስንሶሽ ጫካ ውስጥ ይገባል አንች ደግሞ
እንደ አለቅት ደረቱን እየበሳሽ ሙቅ ልቡ ወስጥ ትገቢና ጎዝጉዘሽ
ትተኛለሽ ልቡ ውስጥ ሆነሽ ጡትሽን ሲዳስሰው ሁለመናሽን ሲያሸው
ለሴት ልጅ ከዚህ የበለጠ ምን ደስታና ጣእም ያለው ህይወት ይኖራታል!" አለች ጎይቲ ያቆመችውን ፀጉር መስራት ለመጀመር ካርለትን ወደ ጉያዋ ሳብ እያደረገቻት።
"ጎይቲ ታዲያ ዱላ ለሐመር ሴት የፍቅር መግለጫ ነው?"
"ይእ! ልጃገረድ ሆነሽ ዳንስ ቦታ የለመድሽው ፍቅር ባልሽ ዘንድ ስትሄጂም የሚጠብቅሽ ፍቅር ዱላ ነው"
"እናንተ አገር የፍቅር መግለጫችሁ ምንድን ነው?"
"መተሳሰብ: መሳሳም …"
"ይእ! ታለ ግርፊያ መተሳሰብ የተኮመታተረው ስሜትሽ ተመታቶ ሳይፍታታ መሳሳም በአፍንጫዬ ይውጣ! ምን ኑሮ ነው
እቴ!"
"ስላለመድሽው እንጂ …"
"ይእ! በይ ዝምበይ
እኔ የሌሎችን ነገርሁሽ እንጂ እኔማ ልምዴን ተገፍፌ እንደ ምትታለብ ላም ዳሌየንና ጡት ስሬን
የሚያሽ ባል አግብቻለሁ" እንዲያው ግን ካርለቴ ከሎ የልምዴን ሰጥቶኝ እንዲህ ማህፀኔ ቢደርቅ እኮ አይከፋኝም ነበር, ከዛሬ ነገ
ወንድ ወንድ ይሸተኛል ስል ከዛሬ ነገ የወንዶችን ለበቅ ያነሳል ስል ዕጣ ፋንታዬ እንዲህ ይክፋ ካርለቴ!" ብላ ምርር ብላ አዘነች
"አዝናለሁ ጎይቲ
ግርፊያ ለሐመር ልጃገረድ እንዲህ እንደ ውቅያኖስ ወለል የጠለቀ ትርጉም ያለው አይመስለኝም ነበር!
ስትላት ጎይቲ ውቅያኖስ ያለችው ባይገባትም
"ይእ! የአባት ደንብ አይደል ካርለቴ እናትሽ ባልሽ ዘንድ
ከመሄድሽ በፊት ባልሽ ሲመታሽ አታልቅሽ የባልሽ ጓደኞች ወደ ቤትሽ ሲመጡ ከጎሽ ቆዳ የተሰራ ጫማቸውን ጠመንጃቸውን ተቀብለሽ ተቀብለሽ ቤት አስገቢ ቀጥለሽ ከውጭ ቁርበት አንጥፈሽ ሸፈሮ ቡና አፍይላቸው" የባልሽን የአደን ጓደኛ ሚሶ'
የዝላይ ወቅት ጓደኛውን ባርግያ በይ በባራዛ አርጩሜ ገርፈው
ምን ተሰማሽ? ሲሉሽ ፈገግ ብለሽ ምንም በያቸው ያን ጊዜ በማርና ወተት ያደገች ተጨዋች ናት ብለው ይግባቡሻል" ለባልሽም
አንችን አሞጋግሰው ስለሚነግሩት ይቀርብሻል"
"ሲመቱሽ ካለቀስሽና አንገትሽን ከደፋሽ ግን ከብትና ፍየል አልጠበቀችም ቀፎ አልሰቀለችም ድሀ አደግ ጨዋታ የማታውቅ
እንደ አነር ቁጡና ክፉ ናት ብለው ይጠሉሻል" ያን ሲሰማ ደግሞ ባልሽም ይጠላሻል ይርቅሻል ውሎው ከሌላ ሴት ጋር ይሆናል እያሉ ዘመዶችሽ መክረውሽ አለት ድንጋይ ልብሽ ውስጥ ጨምረሽ
ጠንካራ እሆናለሁ ብለሽ ባልሽ ዘንድ ሄደሽ የጠበቅሽውን ሁሉ
ስታጭው ምነው አትራቢ ምነው አታዝኝ!" ብላ ጎይቲ እንባዋን ፀጥ ብሎ እንዲፈስ ከፈተችው
ካርለትም ዐይኖችዋ በእንባ እንዳቀረዘዙ ጎይቲን እያባበለች አንድ ቃል በህሊናዋ ብልጭ ብሎ ድርግም አለ ፈለገችው
ያን ቃል ፈረንሳዮች ፍላጀላሲዬን ይሉታል እንግሊዞች ደሞ
ፍላጄሌሽን ደስ አላት ህሊናዋ ከትውስታው ክፍል ጀባ ያላትን ቃል ወደ ኖረበት ተመልሶ ሳይገባ አፈፍ አድርጋ ስለያዘችው
ፍላጀላሲዬን ስርዓት ባለው ወይንም ሃይል በተሞላበት
መንገድ በሃይማኖት ተከታዮች የሚፈፀም ግርፊያ ነው" በብዙ
የሃይማኖት ተቋማት ፍላጀላሲዬን በመባል የሚታወቀው ግርፊያ
የርኩስ መንፈስ የማስወጫ ስልትና መፈወሻ ዘዴ ተደርጎ ይቆጠራል"በጥንት "ዘመን የሚኖሩ ብዙ ሰዎች በግርፊያ መሰቃየትን እንደ
አምልኮዋዊ ፀጋ ይቆጥሩት ነበር በነዚህ ህዝቦች እምነት መገረፍ ወይን በአካላዊ ጉዳት መሰቃየት ከሃጢያታቸው መንፃታቸውን፥ከመቅሰፍት
መዳናቸውን የሚያረጋግጡበት
ሆኖ ሲታመንበት ቆይቷል
በሰሜን አሜሪካ ህንዶች: በስፖርታዎችና በሮማውያን
ግርፊያ የአማልክትን ወይንም የቅድመ አያቶችን
ምስል ጭንብል
ባጠለቀ ገራፊ የሚፈፀም ነበር" ይህ ድርጊት በአስራ ሶስተኛው ክፍለ
ዘመን አጋማሽና በአስራ አራተኛው ክፍለ ዘመንም ቀጥሎ እንደ ጀርመን: ሆላንድ በመሣሰሉት አገሮችም ተስፋፍቶ ቆይቷል በብዙ አገሮች በበዓላት ቀን ወንዶች ጀርባቸውንና ደረታቸውን በአለንጋ
ይገረፋሉ።
ይህ አምልኮዋዊ እምነት እ.ኤ.አ. በ1349 ዓ.ም እንደነበሩት ፓትሪያርክ ክሌመንት በመሳሰሉ የሃይማኖት አባቶች ከረር ያለ ተቃውሞ ግርፊያ እየቀነሰ ቢመጣም በአሁኑ ዘመንም በደቡብ
የአውሮፓ ሀገሮች በላቲን አሜሪካውያንና በመካከለኛውና ሩቅ
ምስራቅ አገሮች የተለመደ ነው ለምሳሌ በታይዋን የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በየአመቱ በስቅለት ቀን እንደ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ መገረፍ: መሰቃየት: እጅና እግርን በሚስማር መቸንከር
የእየሱስ ክርስቶስን ፍቅር እንደ ማግኘት ምድራዊ ሃጢያትን እንደ መቀነስና ለሰማያዊው ህይወት በክብር መዝገብ እንደመመዝገብ
ይቆጠራል
ከዚህ ውጭ ግን ዘመንሁ በሚለው ህብረተሰብ በሁለቱም ፆታ ግርፊያ በብዙ ግለሰቦች የወሲብ ስሜት መቀስቀሻ ወይንም የወሲብ ስሜት ማርኪያ ስልት እንደሆነና የገራፊ ልብሶችና የመግረፊያ
አለንጋዎች የሚሸጡባቸው የወሲብ ሱቆች
በርካታ እየሆኑ
መጥተዋል እኒህ ግርፊያን እንደ ወሲባዊ የችግር መፍትሔ የሚቆጥሩ
ሰዎችን የስነ አዕምሮ ጠቢባን የስነ-አዕምሮ
ችግር ያለባቸው እንደሆኑ በመቁጠር ብዙ መላ ምቶችን እየደረደሩ ቢሆንም
የመገረፍ ፍላጎት ወይንም ሱስ ግን አንድም የተፈጥሮ ባህሪ ውጤት ወይንም እምነት የፈጠረው ፍላጎት ስለመሆኑ አያጠራጥርም ብላ አሰበችና የሐመሩ ግርፊያም ባህላዊ እምነት የፈጠረው የህሊናና
የአካል ዝግጁነት ውጤት ነው ብላ ደመደመች።
እየጨለመ ሲመጣ የእሳቱ ወጋገን ይበልጥ እየጎላ እየጎላ መጣ ወጣቶች ለስነ-ስርዓቱ ከሰበሰቡት እንጨት በተጨማሪ ከጫካ
ግንዲላውን: ጭራሮውን እየተሸከሙ እያመጡ ይከምራሉ ጥቂት ጎረምሶች ደግሞ ለወጠሌ ጥብስ የሚሆነውን ችካል በጩቤያቸው ይጠርባሉ ሌሎች የእድሜ ጓደኛ ጎረምሶች ደግሞ ከሳቱ ርቀው ተሰብስበው ያወጋሉ፤ አንዳንዴም
በተቀቡት ዥንጉርጉር የአኖ ቀለም ከሹልሹላቸው
ለዳንሱ ዝግጅት
የሰጎን ላባ ሰክተው
ጨሌያቸውን አንገታቸው
ላይ ደርድረው ግንባራቸው ላይ የጨሌ ገመድ
ቋጥረው ዳንሱንና ድሪያውን ናፍቀው ውስጥ ለውስጥ ይቋምጣሉ አልደርስ ብሏቸው"
"ሚሶ!" አለ አንዱ
አለ አንዱ ከመሀላቸው የአደን ጓደኞቹን የሰአት ማሳለፍያ ጨዋታ ሊያወጋቸው።
👍25
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አስር
ሽማግሌዎች ከዘርሲዎች አለቃ ጎጆ ፊት ለፊት ቁርበት
ተነጥፎላቸው ሲያወሩ እንደቆዩ ኮቶ ቡና የያዘ ሾርቃ አደለቻቸው"
ካርለት ጎጆው ውስጥ ሆና በቀዳዳ ታያቸዋለች ዘግይታ የወጣችው የጨረቃ ብርሃን ምሽቱን ፍንትው አድርጋ አስውባዋለች ካርለት
በልጅነቷም ሆነ በአፍላ ወጣትነቷ ብዙ ስነ ግጥሞች ስለጨረቃ
ውበት፥ ስለጨረቃ ፍቅር: ስለጨረቃ ስደት ... ተፅፈው አንብባለች
የሰለጠነው ዓለም ግን ፀሐይን እንጂ የጨረቃን ውበት ራሱ በፈበረከው የኤሌክትሪክ ብርሃን ተነጥቋል የጨረቃ ውስጠ ሚስጥር ትዝታውም ተረስቷል ሐመር ላይ ግን ጨረቃ እንደ ጥንቱ ዘመን ሙሉ አቅም: ጥንካሬ ውበት
አላት
ሽማግሎች በጨረቃ ብርሃን ምረቃ ጀመሩ፤ ምኞታቸው
ፍላጎታቸው የጋራ ነው" ሐመሮች አምላካቸውን አያስቸግሩም አንዱ ጤንነት ሌላው ንዋይ ፍቅር . ... እየተመኘ አምላኩን የሚይዘው የሚጨብጠውን
እያሳጣ ግራ አያጋባውም
ሐመሮች ዝናብና ጤንነት
ሁሌም የሚለምኑት ሁለት ነገር ነው ውስን
ብቻ ዝናብ ካለ ሳር አለ ሣር ካለ ከብቶች አሉ ከብቶች ካሉ ይኖራሉ" ሐመር ላይ ቦርጫም ምኞት የለም
የህይወት ልዩነት እንዲኖር የሚፈልግ ወይንም የሚመኝ የለም በእኩልነት እንጂ በልጦ ለመኖር የሚያስብ የለም የቤቱ ቅርፅ አንድ መልክ የቤቱ ዕቃ አንድ አለባበሱ አንድ
ሁሉም አንድ መልክ አለው ሐመር ላይ የተለዬ ያፍራል እንጂ አይኮራም፤ በመለየቱ
ይወቀሳል እንጂ አይከበርም
ሽማግሎች ቡናቸውን እንዲህ ተመራርቀው ከጠጡ በኋላ ወደ
መደነሻው ገላጣ ሜዳ ሄዱ ከተሰባሰበው የመንደሯ ሰው አቅራቢያ ተይዞ የቆመው በሬ ጂራቱን እያጠማዘዘ: ወገቡን እየለመጠ፥አንገቱን እየቀበረ ለማምለጥ ቢሞክርም ቀንድና ቀንዱን፥ ጅራቱን
የያዙት ጎረምሶች ሊያንቀሳቅሱት አልቻሉም
ሽማግሎች ከመረቁና ደልቲን የአባቱን ደንብ በማክበሩ ፕስስ እያሉ ትንፋሻቸውን ካርከፈከፉበት በኋላ የአመጣውን የቅጣት
ከብት ጉሮሮ ከወገቡ ባወጣው ጩቤ ወጋው፤ ደሙ በሾርቃ ተጠራቅሞ
የተወጋውን ከብት ጎረምሶቹ ለቀቁትና ወድቆ ተፈራገጠ ከትንሽ ጊዜ ቆይታ በኋላ ብልቱ እየወጣ ጥብሱ ተጀመረ የተዘጋጀው ከተበላ በኋላ ዳንሱ ቀጠለ ሽማግሎች ከጎረምሶችና
ልጃገረዶች ጋር ሲደንሱና ሲፎክሩ ቆይተው እኩለ ሌሊት አካባቢ
ተጠራርተው የዳንሱን ቦታ ለጎረምሶችና ልጃገረዶች ለቀው ሄዱ ልጃገረዶች በጨሌና ዛጎል የተዋበውን የፍየል ቆዳቸውን እያወናወኑ: አንባራቸውን እያፋጩ ፊታቸው ላይ የተቀቡት የአኖ ቀለም ከጨረቃዋ ብርሃን ጋር እንደ ከብቶች እያንፀባረቀ ሳቃቸው እንደ ከርሰ ምድር የእንፋሎት ውሃ ቡልቅ ፍልቅልቅ ሽቅብ ወደ ወንዶች ጆሮ እየፈሰሰ ጭፈራው ደመቀ
ጎረምሶች ረጋ ብሎ ሲፈስ የነበረውን ዳንስ ሲለውጡት
መአበሉን ሊያስነሱት ፍቅር
በጥቅማ ጥቅም የጠቦት ስብ ያልሆነበትን የፍቅር ገበያ እንዲደራ በአይነት ሰጦ ለመቀበል እንዲቻል
የቦዮን ጎዳና ሊከፍቱት
ዳንስ ሊለውጡት የወንድን ጭን ከሴት ጭን ጋር እያፏጩ የፍቅር
አረፋ ሊያስደፍቁት በማዕበሉ እየተወረወሩ
ነፍሳቸው የመጨረሻውን እርካታ ለቅፅበት ወደምታገኝበት ጫካ
ለመግባት የሚያስችላቸውን ቅላፄ ጀመሩት።
… አንች ከርታታ ከልቡ የሚያስተናግድሽ በአልኮል ፈረስ ሳይጋልብ በጥቅም
ዓይኑ ሳይታወር በምኞት ህሊናው ሳይበሰብስ
በመምሰል ቀሳፊ በሽታ ሳይጠመድ፥ በራስ መተማመኑን አኝኮ
ሳይውጥ ደስታ ሆይ! ከልቡ የሚቀበልሽ ስላለሽ ደስ ይበልሽ' እግዚኦ! በስንቱ አገር: በስንቱ ሰው ሰራሽ አበባ ለማስጌጥ በተሞከረ
ውብ ስፍራ' እየተጠራሽ ዝክር ጠይቀሽ አዝነሽ ተመለሽ! እግዚኦ!
ስንቱ በውሸት ሊያገኝሽ ተንጠራራ አንች ምስኪን ከርታታ ክብርት ደስታ ሆይ! ደስ ይበልሽ እግዚኦ! ... የሚል የመላእክት ማህሌተ
ቡራኬ በዳንሱ አካባቢ
ተሰማት ካርለት
ከርከር ከርከር ዳሌ ወዝወዝ ወገብና አንገት ሰበቅ
ሰበቅ ... እጥፍ እጥፍ፥ ዘርጋ ዘርጋ ዳሌ ወዝወዝ: ሣቅ ሣቅ ሆኖ አሀሀ-ሎሜ!
መባል ተጀመረ ተሟሟቀ የወንዶችና የልጃገረዶች
ሰውነት ልጃገረዶች የሚፈልጉትን ወንድ
እየተወረወሩ እየሄዱ ጋብዘው ወዲያ ወዲህ ሽርር ሽርር … እያሉ
ሲጠብቁ የተመረጡት ወንዶች ወገብ ለወገብ ከጓደኞቻቸው ጋር
ከተያያዙበት እየተላቀቁ እንደ ጎራዴ ምዝዝ: መሬቷን ድልቅ፥ ሸብሸብ ደሞ ዝልል
እያሉ ወደ ጋባዦቻቸው ተጠጉና ወገብ ለወገብ እየተያያዙ ገቡ ባልጩቱ
ተጠልፎ እንደ ኤሌክትሪክ ገመድ ጫፍ ተገናኘ ሞገዱ ተለቀቀ የጡት ጫፍ ሊወርድ እንደተቃረበ ጀት ጎማ ከተጣጠፈበት እየተዘረጋጋ ቆመ ተሳሳለ ቢላዋና ሞረዱ ስለቱ የፍቅር ጮማውን ቆርጦ ወደ የአፋቸው አስጠጋው አላመጡት: አደቀቁት አልመው ዋጡት ያን ምርጥ የሐመር ሰንጋ የፍቅር ጮማ ልብ ቦታውን
እየለቀቀች ዘለለች ህሊና ትዕዛዝ ሰጠ ደስታ ሆይ አንቺ ከርታታ ምስኪን ሆይ ደስ ይበልሽ! ማህሌቱ አላቆመም ካርለት
ይህን ሰማያዊና ምድራዊ የተጣጣመ ትርዒት ፈዛ ስትመለከት ለረጅም ጊዜ ቆየች ኮቶ ከኋላዋ መጥታ ባትነካትማ የምትነቃ
አትመስልም ቅዠት የሌለበት ህልም ... ፍርሃት የሌለበት ደስታ።
"ኮቶ ልትደንሽ ወደ ዳንሱ ገብተሽ ከኋላዬ የምትመጭው ከየት
ነው?" አለቻት ካርለት ዐይን ዐይኖችዋን እያየች
"ይእ! ጥጆችን ሳራክብ እሁ አለፉኝ ሲራከቡ!" ብላ
የካርለትን ትከሻ ተደገፈች "ነው!" ካርለት ገባት የቆየችበት የኮቶ ሰውነት ዛል ብሏል ሰውነቷ እንደ እንቦሳ ሰውነት ያረግዳል
የእርካታ ትንፋሽዋ በመላ ሰውነቷ ይትጎለጎላል
"ኮቶ ደልቲን ልጋብዘው?"
"ይእ! ኧረ ተይ ከእጮኛ ጋርማ አይደነስም እሱ ከፈለገ መጥቶ ሲጠራሽ ባይሆን አጠገቡ ትሄጃለሽ ከዚያ እያወጋችሁ ቀስ
በቀስ ከዳንሱ ቦታ ፈንጠር፥ ፈንጠር ... እያላችሁ በመጨረሻ ጨረቃዋን እፍ' ብላችሁ አሹፋችሁባት ትጠፋላችሁ እሷም ቀልድ
ስለምትወድ እየሳቀች ትከተላችኋለች ካለ ጨረቃ የወንድና ልጃገረድን ፍቅር ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ የሚያውቀው
የለም!"
"የመንደራችን ጎረምሶች ግን ተእንግዲህ ትቀመስ ማለታቸው አይቀርም የአባትሽ ዘመዶች (እንደናሶችም) እንደ እኛ ይገርፉሻል"በይ እቴ ወሬው ይብቃ እንጫወት" ብላ በቆሙበት መወዛወዝ
ጀመሩ"
ደልቲ ከዳንሱ ወጥቶ ካርለት አባት ብላ የመረጠችውን ዘመድ
ረምሳ ጠራውና በርኮታው ላይ ተቀመጠ" ጎረምሳው
ጥሪውን ተቀብሎ አጠገቡ ሄዶ ቁጭ አለ
"ሚሶ!" አለው ደልቲ
"ሚሶ!" አለ ጎረምሳው"
"...ይህችን ልጅ የአባት ወጓን አስተምሯት እንጂ?"
"እእ! - ካርለቴን ነው?"
"አዎ! ከብትና ፍዬል ትጠብቅ ቀፎም ትስቀል ዳንሱ ላይም ግረፏት እንጂ. አሁን ታልሰባች በኋላ እኔ ስንቱን ላርማት ነው?"
"እእ! እሽ ኧረ እኛም ስንመክርበት ነበር እንዳልኸውስ ተሌሎች እህቶቻችን ነጥለን ለምን እናያታለን! ትንሽ
እሚያሰቃጥጠው እንኳን ተገርፋ ሌሎቹ ሲገረፉ ስታይ ንዳድ
እንደያዘው ሰው እየተንቀጠቀጠች መግቢያው ነው የሚጠፋት,,
"አይቻታለሁ ባትለምደው ነው! ግዴለም አስለምዷት
ተዚያ እሷው ያምራታል እሷ እኮ ህፃን ማለት ናት ህፃንን
ብትመታው ያለቅሳል
ሴቷ ግን እድሜ ለአባቷ
ለመንደሯ ጎረምሶች እያደገች ስትሄድ እያየች ትማርና በኋላ በተግባር ደሞ ቀስ በቀስ ትለምዳለች, ትፈራለች ብላችሁ አትተዋት
የኖረችበትን መገመቱ ይከብዳል! እነሱ በድለዋታልና እኛም ግን
ደግመን ልንበድላት አይገባም የዱላን ፍቅር አሳይዋት እሷም ተተወሰነ ጊዜ በኋላ ፍርሃቱ ይወጣላታል!"
"እእ!- እሽ ዛሬስ እኛም አስበናታል ና እንጂ አንተስ
ተጫዋት?"
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አስር
ሽማግሌዎች ከዘርሲዎች አለቃ ጎጆ ፊት ለፊት ቁርበት
ተነጥፎላቸው ሲያወሩ እንደቆዩ ኮቶ ቡና የያዘ ሾርቃ አደለቻቸው"
ካርለት ጎጆው ውስጥ ሆና በቀዳዳ ታያቸዋለች ዘግይታ የወጣችው የጨረቃ ብርሃን ምሽቱን ፍንትው አድርጋ አስውባዋለች ካርለት
በልጅነቷም ሆነ በአፍላ ወጣትነቷ ብዙ ስነ ግጥሞች ስለጨረቃ
ውበት፥ ስለጨረቃ ፍቅር: ስለጨረቃ ስደት ... ተፅፈው አንብባለች
የሰለጠነው ዓለም ግን ፀሐይን እንጂ የጨረቃን ውበት ራሱ በፈበረከው የኤሌክትሪክ ብርሃን ተነጥቋል የጨረቃ ውስጠ ሚስጥር ትዝታውም ተረስቷል ሐመር ላይ ግን ጨረቃ እንደ ጥንቱ ዘመን ሙሉ አቅም: ጥንካሬ ውበት
አላት
ሽማግሎች በጨረቃ ብርሃን ምረቃ ጀመሩ፤ ምኞታቸው
ፍላጎታቸው የጋራ ነው" ሐመሮች አምላካቸውን አያስቸግሩም አንዱ ጤንነት ሌላው ንዋይ ፍቅር . ... እየተመኘ አምላኩን የሚይዘው የሚጨብጠውን
እያሳጣ ግራ አያጋባውም
ሐመሮች ዝናብና ጤንነት
ሁሌም የሚለምኑት ሁለት ነገር ነው ውስን
ብቻ ዝናብ ካለ ሳር አለ ሣር ካለ ከብቶች አሉ ከብቶች ካሉ ይኖራሉ" ሐመር ላይ ቦርጫም ምኞት የለም
የህይወት ልዩነት እንዲኖር የሚፈልግ ወይንም የሚመኝ የለም በእኩልነት እንጂ በልጦ ለመኖር የሚያስብ የለም የቤቱ ቅርፅ አንድ መልክ የቤቱ ዕቃ አንድ አለባበሱ አንድ
ሁሉም አንድ መልክ አለው ሐመር ላይ የተለዬ ያፍራል እንጂ አይኮራም፤ በመለየቱ
ይወቀሳል እንጂ አይከበርም
ሽማግሎች ቡናቸውን እንዲህ ተመራርቀው ከጠጡ በኋላ ወደ
መደነሻው ገላጣ ሜዳ ሄዱ ከተሰባሰበው የመንደሯ ሰው አቅራቢያ ተይዞ የቆመው በሬ ጂራቱን እያጠማዘዘ: ወገቡን እየለመጠ፥አንገቱን እየቀበረ ለማምለጥ ቢሞክርም ቀንድና ቀንዱን፥ ጅራቱን
የያዙት ጎረምሶች ሊያንቀሳቅሱት አልቻሉም
ሽማግሎች ከመረቁና ደልቲን የአባቱን ደንብ በማክበሩ ፕስስ እያሉ ትንፋሻቸውን ካርከፈከፉበት በኋላ የአመጣውን የቅጣት
ከብት ጉሮሮ ከወገቡ ባወጣው ጩቤ ወጋው፤ ደሙ በሾርቃ ተጠራቅሞ
የተወጋውን ከብት ጎረምሶቹ ለቀቁትና ወድቆ ተፈራገጠ ከትንሽ ጊዜ ቆይታ በኋላ ብልቱ እየወጣ ጥብሱ ተጀመረ የተዘጋጀው ከተበላ በኋላ ዳንሱ ቀጠለ ሽማግሎች ከጎረምሶችና
ልጃገረዶች ጋር ሲደንሱና ሲፎክሩ ቆይተው እኩለ ሌሊት አካባቢ
ተጠራርተው የዳንሱን ቦታ ለጎረምሶችና ልጃገረዶች ለቀው ሄዱ ልጃገረዶች በጨሌና ዛጎል የተዋበውን የፍየል ቆዳቸውን እያወናወኑ: አንባራቸውን እያፋጩ ፊታቸው ላይ የተቀቡት የአኖ ቀለም ከጨረቃዋ ብርሃን ጋር እንደ ከብቶች እያንፀባረቀ ሳቃቸው እንደ ከርሰ ምድር የእንፋሎት ውሃ ቡልቅ ፍልቅልቅ ሽቅብ ወደ ወንዶች ጆሮ እየፈሰሰ ጭፈራው ደመቀ
ጎረምሶች ረጋ ብሎ ሲፈስ የነበረውን ዳንስ ሲለውጡት
መአበሉን ሊያስነሱት ፍቅር
በጥቅማ ጥቅም የጠቦት ስብ ያልሆነበትን የፍቅር ገበያ እንዲደራ በአይነት ሰጦ ለመቀበል እንዲቻል
የቦዮን ጎዳና ሊከፍቱት
ዳንስ ሊለውጡት የወንድን ጭን ከሴት ጭን ጋር እያፏጩ የፍቅር
አረፋ ሊያስደፍቁት በማዕበሉ እየተወረወሩ
ነፍሳቸው የመጨረሻውን እርካታ ለቅፅበት ወደምታገኝበት ጫካ
ለመግባት የሚያስችላቸውን ቅላፄ ጀመሩት።
… አንች ከርታታ ከልቡ የሚያስተናግድሽ በአልኮል ፈረስ ሳይጋልብ በጥቅም
ዓይኑ ሳይታወር በምኞት ህሊናው ሳይበሰብስ
በመምሰል ቀሳፊ በሽታ ሳይጠመድ፥ በራስ መተማመኑን አኝኮ
ሳይውጥ ደስታ ሆይ! ከልቡ የሚቀበልሽ ስላለሽ ደስ ይበልሽ' እግዚኦ! በስንቱ አገር: በስንቱ ሰው ሰራሽ አበባ ለማስጌጥ በተሞከረ
ውብ ስፍራ' እየተጠራሽ ዝክር ጠይቀሽ አዝነሽ ተመለሽ! እግዚኦ!
ስንቱ በውሸት ሊያገኝሽ ተንጠራራ አንች ምስኪን ከርታታ ክብርት ደስታ ሆይ! ደስ ይበልሽ እግዚኦ! ... የሚል የመላእክት ማህሌተ
ቡራኬ በዳንሱ አካባቢ
ተሰማት ካርለት
ከርከር ከርከር ዳሌ ወዝወዝ ወገብና አንገት ሰበቅ
ሰበቅ ... እጥፍ እጥፍ፥ ዘርጋ ዘርጋ ዳሌ ወዝወዝ: ሣቅ ሣቅ ሆኖ አሀሀ-ሎሜ!
መባል ተጀመረ ተሟሟቀ የወንዶችና የልጃገረዶች
ሰውነት ልጃገረዶች የሚፈልጉትን ወንድ
እየተወረወሩ እየሄዱ ጋብዘው ወዲያ ወዲህ ሽርር ሽርር … እያሉ
ሲጠብቁ የተመረጡት ወንዶች ወገብ ለወገብ ከጓደኞቻቸው ጋር
ከተያያዙበት እየተላቀቁ እንደ ጎራዴ ምዝዝ: መሬቷን ድልቅ፥ ሸብሸብ ደሞ ዝልል
እያሉ ወደ ጋባዦቻቸው ተጠጉና ወገብ ለወገብ እየተያያዙ ገቡ ባልጩቱ
ተጠልፎ እንደ ኤሌክትሪክ ገመድ ጫፍ ተገናኘ ሞገዱ ተለቀቀ የጡት ጫፍ ሊወርድ እንደተቃረበ ጀት ጎማ ከተጣጠፈበት እየተዘረጋጋ ቆመ ተሳሳለ ቢላዋና ሞረዱ ስለቱ የፍቅር ጮማውን ቆርጦ ወደ የአፋቸው አስጠጋው አላመጡት: አደቀቁት አልመው ዋጡት ያን ምርጥ የሐመር ሰንጋ የፍቅር ጮማ ልብ ቦታውን
እየለቀቀች ዘለለች ህሊና ትዕዛዝ ሰጠ ደስታ ሆይ አንቺ ከርታታ ምስኪን ሆይ ደስ ይበልሽ! ማህሌቱ አላቆመም ካርለት
ይህን ሰማያዊና ምድራዊ የተጣጣመ ትርዒት ፈዛ ስትመለከት ለረጅም ጊዜ ቆየች ኮቶ ከኋላዋ መጥታ ባትነካትማ የምትነቃ
አትመስልም ቅዠት የሌለበት ህልም ... ፍርሃት የሌለበት ደስታ።
"ኮቶ ልትደንሽ ወደ ዳንሱ ገብተሽ ከኋላዬ የምትመጭው ከየት
ነው?" አለቻት ካርለት ዐይን ዐይኖችዋን እያየች
"ይእ! ጥጆችን ሳራክብ እሁ አለፉኝ ሲራከቡ!" ብላ
የካርለትን ትከሻ ተደገፈች "ነው!" ካርለት ገባት የቆየችበት የኮቶ ሰውነት ዛል ብሏል ሰውነቷ እንደ እንቦሳ ሰውነት ያረግዳል
የእርካታ ትንፋሽዋ በመላ ሰውነቷ ይትጎለጎላል
"ኮቶ ደልቲን ልጋብዘው?"
"ይእ! ኧረ ተይ ከእጮኛ ጋርማ አይደነስም እሱ ከፈለገ መጥቶ ሲጠራሽ ባይሆን አጠገቡ ትሄጃለሽ ከዚያ እያወጋችሁ ቀስ
በቀስ ከዳንሱ ቦታ ፈንጠር፥ ፈንጠር ... እያላችሁ በመጨረሻ ጨረቃዋን እፍ' ብላችሁ አሹፋችሁባት ትጠፋላችሁ እሷም ቀልድ
ስለምትወድ እየሳቀች ትከተላችኋለች ካለ ጨረቃ የወንድና ልጃገረድን ፍቅር ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ የሚያውቀው
የለም!"
"የመንደራችን ጎረምሶች ግን ተእንግዲህ ትቀመስ ማለታቸው አይቀርም የአባትሽ ዘመዶች (እንደናሶችም) እንደ እኛ ይገርፉሻል"በይ እቴ ወሬው ይብቃ እንጫወት" ብላ በቆሙበት መወዛወዝ
ጀመሩ"
ደልቲ ከዳንሱ ወጥቶ ካርለት አባት ብላ የመረጠችውን ዘመድ
ረምሳ ጠራውና በርኮታው ላይ ተቀመጠ" ጎረምሳው
ጥሪውን ተቀብሎ አጠገቡ ሄዶ ቁጭ አለ
"ሚሶ!" አለው ደልቲ
"ሚሶ!" አለ ጎረምሳው"
"...ይህችን ልጅ የአባት ወጓን አስተምሯት እንጂ?"
"እእ! - ካርለቴን ነው?"
"አዎ! ከብትና ፍዬል ትጠብቅ ቀፎም ትስቀል ዳንሱ ላይም ግረፏት እንጂ. አሁን ታልሰባች በኋላ እኔ ስንቱን ላርማት ነው?"
"እእ! እሽ ኧረ እኛም ስንመክርበት ነበር እንዳልኸውስ ተሌሎች እህቶቻችን ነጥለን ለምን እናያታለን! ትንሽ
እሚያሰቃጥጠው እንኳን ተገርፋ ሌሎቹ ሲገረፉ ስታይ ንዳድ
እንደያዘው ሰው እየተንቀጠቀጠች መግቢያው ነው የሚጠፋት,,
"አይቻታለሁ ባትለምደው ነው! ግዴለም አስለምዷት
ተዚያ እሷው ያምራታል እሷ እኮ ህፃን ማለት ናት ህፃንን
ብትመታው ያለቅሳል
ሴቷ ግን እድሜ ለአባቷ
ለመንደሯ ጎረምሶች እያደገች ስትሄድ እያየች ትማርና በኋላ በተግባር ደሞ ቀስ በቀስ ትለምዳለች, ትፈራለች ብላችሁ አትተዋት
የኖረችበትን መገመቱ ይከብዳል! እነሱ በድለዋታልና እኛም ግን
ደግመን ልንበድላት አይገባም የዱላን ፍቅር አሳይዋት እሷም ተተወሰነ ጊዜ በኋላ ፍርሃቱ ይወጣላታል!"
"እእ!- እሽ ዛሬስ እኛም አስበናታል ና እንጂ አንተስ
ተጫዋት?"
👍29❤2😢2
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
...ደግመን ልንበድላት አይገባም የዱላን ፍቅር አሳይዋት እሷም ተተወሰነ ጊዜ በኋላ ፍርሃቱ ይወጣላታል!"
"እእ! እሽ ዛሬስ እኛም አስበናታል ና እንጂ አንተስ
ተጫዋት?"
አለሁ የት እሄዳለሁ አዳሬ ተዚሁ ነው" ብሎ ደልቲ
ከበርኮታው ላይ ተነሳ ጎረምሳው ደግሞ የባራዛ አርጩሜውን ወደ
ደበቁበት ጉቶ ሄዶ ሶስት ለበቆችን አነሳ ደልቲም ከወንዶች ግማሽ ክብ ሰልፍ ገብቶ ወገብ ለወገብ ተያያዘ
አንዱ ጎረምሳ አንደ መፎከሪያ በርኮታውን በቀኝ እጁ ይዞ የመፎከሪያ በሬውን ጥንካሬና ውበት የጓደኝነታቸውን ምሥጢር
ሲደረድር ሁለት ልጃገረዶች አንባራቸውን እያፋጩ: ከፊት ለፊቱ ቆመው ሲያሞጋግሱት ቆይቶ እያቀነቀነ መዝለልና መጨፈር ጀመረ
ከዚያ የእድሜ ጓደኞቹ ተቃቅፈው ሄደው በቃህ ብለው በትህትና
ጠይቀው አጅበው ተሰልፉ አስገቡት ወዲያው ግን
ጧ ጧ፥ጣጣ.ጣ… የሚል ግርፊያ ተሰማና ልጃገረዶች እያውካኩ፥ ብትን ብለው ሲስቁ ቀጭን የሲቃ ልቅሶ ከመካከላቸው ተሰማ"
ያች ባለጌ ናት! አለ ደልቲ ንድድ እያለው"
ኮቶ ምን አደረኩት ..." ካርለት እንባዋ እየረገፈ ሰውነቷ
እየተንቀጠቀጠ፥ ኮቶን ተጠምጥማ ጠየቀቻት ለበለባት የተገረፈችው
ቦታ ሰንበሩ ጀርባዋ ላይ እንደ እባብ ተጋድሞ ቆጠቆጣት እንባዋ
እርግፍ እርግፍ አለ
"ኮቶ ለምን ገረፉኝ ..." አለቻት ህቅ ብላ እያለቀሰች,
"ይእ! ካርለቴ ደንብ ነው ብየሽ! ዘመድሽኮ ነው፤ “ለምን ተኔ ጋር አትደንሽም ብሎ ነው የመታሽ ሄደሽ አብረሽው ደንሽ
ይልቅ ታለበለዚያ ይደግምሻል"" ስትላት ካርለት ቦታውን ለቃ
ልትሄድ አሰበች ህሊናዋ ተሟገተ
"ኮቶ ለምን እገረፋለሁ!- እኔ'ኮ መመታት አለመድሁም?" ብላ
በቀላው ዐይኗ ትክ ብላ አየቻት
"ይእ! ስንወለድ እኮ እኛም አለመድነውም ትርጉሙን
ስናውቅ ማድረግ ያለብን ነው ብለን ስናምን ልባችን ደንድኖ ለመድነው አንችስ ሰው መስለሽኝ ስትመጭ የካሮ አፈር ፈጭተሽ መች ትቀቢ ነበር ቆዳ መልበስ:
በእግር መሄድ እንጨት
መልቀም የተማርሽው እዚህ አይደል ግርፊያም የሚለመደው ስትደፍሪ ነው
የፍቅር ማባያ ይሆንሻል
የተማርሽው እዚህ አይደል
ስትገረፊ መጀመሪያ እንደቃሪያ ያቃጥልሻል ቀጥሎ የፍቅር ማባያ ይሆንሻል በመጨረሻ ደግሞ የሚለበልበው ቃሪያ
ያምርሻል! አይዞሽ የኔ እህት ያን ጊዜ እንደ ሱስ በልቦናሽ
ውል እያለ አምጭ አምጭ' እያለ ተሐመር አንበሶች ክርን ስር ያልወሰውስሻል
ከዚያ ትለምጅዋለሽ" ብላ ደረቷ ላይ አስጠግታ አግባባቻት,
"እሽ ኮቶ ካርለት በጽሞና ስታዳምጣት ቆይታ እንባና ሳቋ ተቀላቀለባት
"እሽ! ዓላማ ታውቂያለሽ ኮቶ" አለቻት ትክ ብላ በጨረቃ ብርሃን እያየቻት
"ይእ! ኢላማ ማለትሽ ነው ማነጣጠሪያ የዓልሞ ተኳሽ
መለያ ነው ኢላማ ተሆነ "
"ልክ ነሽ! የአነጣጠርኩት: ዓልሜ የምመታው ኢላማ አለኝ ኮቶ! ስለዚህ
"ይእ! አይ ካርለቴ መቼም የአንች ነገር እንደ እርጎ ዝንብ ወንዶች መዋያ ጥብሉቅ ማለት ስትወጂ እስቲ እንደ ሴት ኢላማሽ
ልጅ መውለድ: ለባል ታዛዥ ለመሆን ይሁን የአባት ደንብ ለማክበር ይሁን ኢላማሽ!"
"እንደንስ ኮቶ! ዳንስ አማረኝ ግርፊያ ፈለግሁኝ... ንኪው ልቤን የፍርሃት እርግጫውን አቆመ
አደፋፈርሽው አስተማርሽው ህዋን የሰው ልጅ በእግሩ ሲረግጥ እኔም በጭንቅላቴ
የመሬትን እንብርት እነካዋለሁ…ቃሪያውን እየበላሁ ጥቅምና
ጉዳቱን ለሌላው አሳያለሁ እነ ዲያና ፎሲ ከጉሬላ ጋር ቅጠል በልተውስ ኖረው የለ
"ይእ!- ካርለቴ!" ወዘወዘቻት ትከሻዋን"
"ደህና ነኝ ኮቶ"
"እየቃዠሽ! ቢጫ ሐሞት እንደሚያስተፋ ወባ እንደያዘው ሰው
"የለም ደህና ነኝ ቃል ኪዳን ነው ኮቶ ሰው ለመሆን፥
ጠንካራ ሰው!... በተሰጠኝ የሰውነት ክፍል ሁሉ ተጠቅሜ ከቦርጆ
ወቀሳ ለመዳን ባህሉ ተጠየቀኝ ለዓላማዬ ስል እኔም የእባብንም
አንገት አንቄ ጥርሶቹን ላይ መርዛም ነው የሚባለውን እባብ ጥቅምና
ጉዳቱን ጉሮሮውን ፈልቅቄ ላይ ተገርፌ፥ አልቅሼ: ቧጥጬ ባህሌን ጥሼ ባህል ላሳውቅ ኮቶ!"
"ይእ! መንደር እንሂድ ካርለቴ?"z
"ተይኝ! ትንሽ ጊዜ ብቻዬን ተይኝ! እሽ?"
"ይእ! እሽ " ኮቶ ሄደች ዝምታ ፀጥታ ህሊናን
እንዳይደነብር እንደሚያረጋጋ ተከብቶች ከአባቷ ከመንደሯ…
ተምራለችና ሄደች
ካርለት ራሷን ከፈተችው... ወደ ራሷ ገባች ... የላላውን
አጠባበቀች የተወጠረውን አላላች የአበጠውን አፈረጠች የቆሸሸውን አፀዳች ካርለት እንደ አዳኝ ውሻ ዐይኗን ጠበብ አድርጋ ደልቲን አየችው አያያትም" ወደ ዳንሱም ልትጋብዘው አትችልም፤ ዳንሱ
እንደገና ተጋጋለ
"ይእ! ካርለቴ ነይ ጋብዥው የገረፈሽን?" ብላ ኮቶ ጠራቻት ወገባቸውን ተቃቀፉ ከዚያ በቄንጥ እንደ ፔንዱለም ፊትና ኋላ
ተወዛወዙና ሶሰት ጊዜ ዘለል: ወዝወዝ… ብለው ሾረው ሄደው ሁለት
ጎረምሶችን ጋበዙ"
የገረፋት ጎረምሳ ካርለት ስትጋብዘው እየሰገረ ሄዶ የካርለትን ጭኖች እንደ መሮ እየሰረሰረ ገብቶ: በእጆቹ ቀጭኑን ወገቧን
ጨምድዶ አሻት ጎረምሳው ሳያቋርጥ እየሰረሰራት ጭኖችዋን በስቶ
ገባ "የት ሊደርስ ነው?" እያለች ሸሸችው እሱ ግን
ወገቧን የጨመደደበትን እጁን እየወጠረ ሲጠጋት ቆየና ከገለዋ ተጣበቀ
የሚታሸው አካሏ የአምቦ ውሃ እንደጠጣ ሰው አስገሳት እሷም
ሰረሰረችው፥ ወዘወዘችው.
ካርለት ያላየች መስላ ደልቲን አየችው ደስ ብሎታል እሷም ደስ አላት ደልቲ አልቀናም ቅናት ባህል እንጂ ተፈጥሯዊ
እንዳልሆነ አሰበች ጭፈራው ቀጠለ ጨዋታው ደመቀ።
"ኮቶ!"
"ዬ ሳቀች ከትከት ብላ ቀጣዩ ዳንስ እስኪጀመር
ቦታቸው ሲመለሱ
"ምን ሆንሽ ካርለቴ?" አለቻት
ሃሣቧን ሳትጨርስው ደልቲ እጅዋን ያዝ አድርጎ
ከሴቶች መሐል ጠራት የሆነ ነገር እንደ ፍላፃ ተወርውሮ ስሜቷን
አጋጋለው" ፈገግ አለችለት ለስሜቷ-ለደልቲ…
ከዚያ በኋላ ብዙ አልተነጋገሩም ቀስ ቀስ እያሉ ፈንጠር ፈንጠር ብለው ጨረቃን አሹፈውባት ሰማይ ይግቡ መሬት ጠፉ….የኢቫንጋዲ ጭፈራው ግን ቀጥሏል ወደፊትም ለቀናት: ለዓመታት ይቀጥል ይሆናል ከዚያ ግን ይሸነቆራል
ወይንም ለዘመናት
ጥቅም፥ ገንዘብ‥ የተባለው ቆሻሻ ስልክልክ ብሎ ገብቶ ይበክለዋል ደስታም ጥቁር ከል ለብሳ: ተስፋ ቆርጣ: መባዘኗን ትጀምራለች
ካልያም አንድዬ አንች ከርታታ ተዛሬ ጀምሮ መባዘንሽ ያቆማል'
ብሎ ይጠራታል… እግዚኦ ያች ቀን ምናለ ባትደርስ! እግዚኦ!…
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቀትር ነው፤ የፀሐይዋ ሙቀት አሸዋው ላይ ነጥሮ እንደ ሐይቅ
ማዕበል እየተንቀሳቀሰ ከርቀት ጀምሮ ይታያል በዚያ አይነቱ ሐሩር የዛፍ ጥላ ህይወት አዳኝ ነው" የሐመር ወንዶች በእንዲህ ዓይነቱ ሙቀት ወቅት ዛፍ ጥላ ሥር ይሄዱና ሲጫወቱ: ሲወያዩ
ቆይተው አሸዋውን ይደለድሉና በበርኮታቸው ጭንቅላታቸውን ደገፍ
አድርገው እረፍት መውሰድ የተለመደ ነው
የሐመር ህይወት የሆነው ከስኬ ወንዝ ከጥም አርኪነቱ ሌላ ከለላ ችግርን መፍቻ በከብት ዝላይ ወቅት የልጃገረዶች መገረፊያ
መጋጌጫ… ማረፊያ ነው ለሰውም ለከብቱም ጫርጫር ሲደረግ ውስጡ ውኃ ይፈልቃል ላዩ መኝታ ይሆናል መወያያ መድረክም ነው ሐመሮች የከስኬ ናቸው ከስኬም የነሱ ነው ያጌጡበታል
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
...ደግመን ልንበድላት አይገባም የዱላን ፍቅር አሳይዋት እሷም ተተወሰነ ጊዜ በኋላ ፍርሃቱ ይወጣላታል!"
"እእ! እሽ ዛሬስ እኛም አስበናታል ና እንጂ አንተስ
ተጫዋት?"
አለሁ የት እሄዳለሁ አዳሬ ተዚሁ ነው" ብሎ ደልቲ
ከበርኮታው ላይ ተነሳ ጎረምሳው ደግሞ የባራዛ አርጩሜውን ወደ
ደበቁበት ጉቶ ሄዶ ሶስት ለበቆችን አነሳ ደልቲም ከወንዶች ግማሽ ክብ ሰልፍ ገብቶ ወገብ ለወገብ ተያያዘ
አንዱ ጎረምሳ አንደ መፎከሪያ በርኮታውን በቀኝ እጁ ይዞ የመፎከሪያ በሬውን ጥንካሬና ውበት የጓደኝነታቸውን ምሥጢር
ሲደረድር ሁለት ልጃገረዶች አንባራቸውን እያፋጩ: ከፊት ለፊቱ ቆመው ሲያሞጋግሱት ቆይቶ እያቀነቀነ መዝለልና መጨፈር ጀመረ
ከዚያ የእድሜ ጓደኞቹ ተቃቅፈው ሄደው በቃህ ብለው በትህትና
ጠይቀው አጅበው ተሰልፉ አስገቡት ወዲያው ግን
ጧ ጧ፥ጣጣ.ጣ… የሚል ግርፊያ ተሰማና ልጃገረዶች እያውካኩ፥ ብትን ብለው ሲስቁ ቀጭን የሲቃ ልቅሶ ከመካከላቸው ተሰማ"
ያች ባለጌ ናት! አለ ደልቲ ንድድ እያለው"
ኮቶ ምን አደረኩት ..." ካርለት እንባዋ እየረገፈ ሰውነቷ
እየተንቀጠቀጠ፥ ኮቶን ተጠምጥማ ጠየቀቻት ለበለባት የተገረፈችው
ቦታ ሰንበሩ ጀርባዋ ላይ እንደ እባብ ተጋድሞ ቆጠቆጣት እንባዋ
እርግፍ እርግፍ አለ
"ኮቶ ለምን ገረፉኝ ..." አለቻት ህቅ ብላ እያለቀሰች,
"ይእ! ካርለቴ ደንብ ነው ብየሽ! ዘመድሽኮ ነው፤ “ለምን ተኔ ጋር አትደንሽም ብሎ ነው የመታሽ ሄደሽ አብረሽው ደንሽ
ይልቅ ታለበለዚያ ይደግምሻል"" ስትላት ካርለት ቦታውን ለቃ
ልትሄድ አሰበች ህሊናዋ ተሟገተ
"ኮቶ ለምን እገረፋለሁ!- እኔ'ኮ መመታት አለመድሁም?" ብላ
በቀላው ዐይኗ ትክ ብላ አየቻት
"ይእ! ስንወለድ እኮ እኛም አለመድነውም ትርጉሙን
ስናውቅ ማድረግ ያለብን ነው ብለን ስናምን ልባችን ደንድኖ ለመድነው አንችስ ሰው መስለሽኝ ስትመጭ የካሮ አፈር ፈጭተሽ መች ትቀቢ ነበር ቆዳ መልበስ:
በእግር መሄድ እንጨት
መልቀም የተማርሽው እዚህ አይደል ግርፊያም የሚለመደው ስትደፍሪ ነው
የፍቅር ማባያ ይሆንሻል
የተማርሽው እዚህ አይደል
ስትገረፊ መጀመሪያ እንደቃሪያ ያቃጥልሻል ቀጥሎ የፍቅር ማባያ ይሆንሻል በመጨረሻ ደግሞ የሚለበልበው ቃሪያ
ያምርሻል! አይዞሽ የኔ እህት ያን ጊዜ እንደ ሱስ በልቦናሽ
ውል እያለ አምጭ አምጭ' እያለ ተሐመር አንበሶች ክርን ስር ያልወሰውስሻል
ከዚያ ትለምጅዋለሽ" ብላ ደረቷ ላይ አስጠግታ አግባባቻት,
"እሽ ኮቶ ካርለት በጽሞና ስታዳምጣት ቆይታ እንባና ሳቋ ተቀላቀለባት
"እሽ! ዓላማ ታውቂያለሽ ኮቶ" አለቻት ትክ ብላ በጨረቃ ብርሃን እያየቻት
"ይእ! ኢላማ ማለትሽ ነው ማነጣጠሪያ የዓልሞ ተኳሽ
መለያ ነው ኢላማ ተሆነ "
"ልክ ነሽ! የአነጣጠርኩት: ዓልሜ የምመታው ኢላማ አለኝ ኮቶ! ስለዚህ
"ይእ! አይ ካርለቴ መቼም የአንች ነገር እንደ እርጎ ዝንብ ወንዶች መዋያ ጥብሉቅ ማለት ስትወጂ እስቲ እንደ ሴት ኢላማሽ
ልጅ መውለድ: ለባል ታዛዥ ለመሆን ይሁን የአባት ደንብ ለማክበር ይሁን ኢላማሽ!"
"እንደንስ ኮቶ! ዳንስ አማረኝ ግርፊያ ፈለግሁኝ... ንኪው ልቤን የፍርሃት እርግጫውን አቆመ
አደፋፈርሽው አስተማርሽው ህዋን የሰው ልጅ በእግሩ ሲረግጥ እኔም በጭንቅላቴ
የመሬትን እንብርት እነካዋለሁ…ቃሪያውን እየበላሁ ጥቅምና
ጉዳቱን ለሌላው አሳያለሁ እነ ዲያና ፎሲ ከጉሬላ ጋር ቅጠል በልተውስ ኖረው የለ
"ይእ!- ካርለቴ!" ወዘወዘቻት ትከሻዋን"
"ደህና ነኝ ኮቶ"
"እየቃዠሽ! ቢጫ ሐሞት እንደሚያስተፋ ወባ እንደያዘው ሰው
"የለም ደህና ነኝ ቃል ኪዳን ነው ኮቶ ሰው ለመሆን፥
ጠንካራ ሰው!... በተሰጠኝ የሰውነት ክፍል ሁሉ ተጠቅሜ ከቦርጆ
ወቀሳ ለመዳን ባህሉ ተጠየቀኝ ለዓላማዬ ስል እኔም የእባብንም
አንገት አንቄ ጥርሶቹን ላይ መርዛም ነው የሚባለውን እባብ ጥቅምና
ጉዳቱን ጉሮሮውን ፈልቅቄ ላይ ተገርፌ፥ አልቅሼ: ቧጥጬ ባህሌን ጥሼ ባህል ላሳውቅ ኮቶ!"
"ይእ! መንደር እንሂድ ካርለቴ?"z
"ተይኝ! ትንሽ ጊዜ ብቻዬን ተይኝ! እሽ?"
"ይእ! እሽ " ኮቶ ሄደች ዝምታ ፀጥታ ህሊናን
እንዳይደነብር እንደሚያረጋጋ ተከብቶች ከአባቷ ከመንደሯ…
ተምራለችና ሄደች
ካርለት ራሷን ከፈተችው... ወደ ራሷ ገባች ... የላላውን
አጠባበቀች የተወጠረውን አላላች የአበጠውን አፈረጠች የቆሸሸውን አፀዳች ካርለት እንደ አዳኝ ውሻ ዐይኗን ጠበብ አድርጋ ደልቲን አየችው አያያትም" ወደ ዳንሱም ልትጋብዘው አትችልም፤ ዳንሱ
እንደገና ተጋጋለ
"ይእ! ካርለቴ ነይ ጋብዥው የገረፈሽን?" ብላ ኮቶ ጠራቻት ወገባቸውን ተቃቀፉ ከዚያ በቄንጥ እንደ ፔንዱለም ፊትና ኋላ
ተወዛወዙና ሶሰት ጊዜ ዘለል: ወዝወዝ… ብለው ሾረው ሄደው ሁለት
ጎረምሶችን ጋበዙ"
የገረፋት ጎረምሳ ካርለት ስትጋብዘው እየሰገረ ሄዶ የካርለትን ጭኖች እንደ መሮ እየሰረሰረ ገብቶ: በእጆቹ ቀጭኑን ወገቧን
ጨምድዶ አሻት ጎረምሳው ሳያቋርጥ እየሰረሰራት ጭኖችዋን በስቶ
ገባ "የት ሊደርስ ነው?" እያለች ሸሸችው እሱ ግን
ወገቧን የጨመደደበትን እጁን እየወጠረ ሲጠጋት ቆየና ከገለዋ ተጣበቀ
የሚታሸው አካሏ የአምቦ ውሃ እንደጠጣ ሰው አስገሳት እሷም
ሰረሰረችው፥ ወዘወዘችው.
ካርለት ያላየች መስላ ደልቲን አየችው ደስ ብሎታል እሷም ደስ አላት ደልቲ አልቀናም ቅናት ባህል እንጂ ተፈጥሯዊ
እንዳልሆነ አሰበች ጭፈራው ቀጠለ ጨዋታው ደመቀ።
"ኮቶ!"
"ዬ ሳቀች ከትከት ብላ ቀጣዩ ዳንስ እስኪጀመር
ቦታቸው ሲመለሱ
"ምን ሆንሽ ካርለቴ?" አለቻት
ሃሣቧን ሳትጨርስው ደልቲ እጅዋን ያዝ አድርጎ
ከሴቶች መሐል ጠራት የሆነ ነገር እንደ ፍላፃ ተወርውሮ ስሜቷን
አጋጋለው" ፈገግ አለችለት ለስሜቷ-ለደልቲ…
ከዚያ በኋላ ብዙ አልተነጋገሩም ቀስ ቀስ እያሉ ፈንጠር ፈንጠር ብለው ጨረቃን አሹፈውባት ሰማይ ይግቡ መሬት ጠፉ….የኢቫንጋዲ ጭፈራው ግን ቀጥሏል ወደፊትም ለቀናት: ለዓመታት ይቀጥል ይሆናል ከዚያ ግን ይሸነቆራል
ወይንም ለዘመናት
ጥቅም፥ ገንዘብ‥ የተባለው ቆሻሻ ስልክልክ ብሎ ገብቶ ይበክለዋል ደስታም ጥቁር ከል ለብሳ: ተስፋ ቆርጣ: መባዘኗን ትጀምራለች
ካልያም አንድዬ አንች ከርታታ ተዛሬ ጀምሮ መባዘንሽ ያቆማል'
ብሎ ይጠራታል… እግዚኦ ያች ቀን ምናለ ባትደርስ! እግዚኦ!…
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቀትር ነው፤ የፀሐይዋ ሙቀት አሸዋው ላይ ነጥሮ እንደ ሐይቅ
ማዕበል እየተንቀሳቀሰ ከርቀት ጀምሮ ይታያል በዚያ አይነቱ ሐሩር የዛፍ ጥላ ህይወት አዳኝ ነው" የሐመር ወንዶች በእንዲህ ዓይነቱ ሙቀት ወቅት ዛፍ ጥላ ሥር ይሄዱና ሲጫወቱ: ሲወያዩ
ቆይተው አሸዋውን ይደለድሉና በበርኮታቸው ጭንቅላታቸውን ደገፍ
አድርገው እረፍት መውሰድ የተለመደ ነው
የሐመር ህይወት የሆነው ከስኬ ወንዝ ከጥም አርኪነቱ ሌላ ከለላ ችግርን መፍቻ በከብት ዝላይ ወቅት የልጃገረዶች መገረፊያ
መጋጌጫ… ማረፊያ ነው ለሰውም ለከብቱም ጫርጫር ሲደረግ ውስጡ ውኃ ይፈልቃል ላዩ መኝታ ይሆናል መወያያ መድረክም ነው ሐመሮች የከስኬ ናቸው ከስኬም የነሱ ነው ያጌጡበታል
👍25🔥1