#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ከፕሎሜ ጎዳና ላይ ያለ ቤት
ፕሎሜ ከተባለ ጎዳና ላይ ንብረትነቱ የመንግሥት ባለሥልጣን የሆነ ባለአንድ ፎቅ ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሁለት ክፍል ቤት ከፎቁ ላይ፣ ሁለት ክፍል
ደግሞ ከምድር ቤት ነበረው፡፡ በተጨማሪ እንደ ወጥ ቤት የሚያገለግል ተጨማሪ ክፍል ፎቁ ላይ ነበረው:: ከዋናው ጎዳና ጋር የተያያዘ ትልቅ የውጭ በር ሲኖረው በአበባ ያጌጠ ሰፊ ግቢ አለው:: ከበስተጓሮው እንደ
እቃና ማድቤቶች ሊጠቅሙ የሚችሉ ሌሎች ሦስት ክፍሎች ነበሩ:: በጓሮ በኩል ደግሞ የምሥጢር በር አለው::
ምስጢሩን ለሚያውቅ እንጂ ይህ
በር፣ በር መሆኑ በቀላሉ አይታይም:: ቤቱ ብዙ ጊዜ ሰው አይከራየውም::
በ1829 ዓ.ም አንድ በእድሜ በሰል ያለ ሰው መጥቶ ይህን ቤት
ይከራየዋል፡፡ ሰውዬው ብቻውን አልነበረም:: አንዲት ወጣት አብራው ነበረች፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ወጣትዋ ልጅ ደግሞ ኮዜት ናት፡፡ ቀደም ሲል ዣን ቫልዣ ይረዳት የነበረችው አሮጊት ደግሞ አብራቸው ናት:: ስምዋ ቱሴይ ይባላል:: ዣን ቫልዣ ቤቱን የተከራየው መሴይ ፎሽለማ በሚል ስም ነው::
ዣን ቫልዣ ለረጅም ጊዜ የኖረበትን ገዳም ለቅቆ ከወጣ በኋላ ምን
ተፈጸመ ቢባል ምንም የሆነ ነገር የለም:: እንደሚታወሰው ዣን ቫልዣ ገዳሙ ውስጥ ደስ ብሎት ነበር የሚኖረው:: በየቀኑ፡ ኮዜትን ያገኛታል።በተገናኙ ቁጥር ፍቅራቸው እየጠናና የአባትነት ስሜቱ እየዳበረ ይሄዳል፡፡
ልጅትዋን ፈጣሪ የሰጠው ፀጋ እንደሆነች ከማነ ባሻገር ይህችን ልጅ ከእርሱ ማንም ሊለያት እንደማይችል ገምቷል:: እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ከእርሱ የማትለይ ፍጡር ለመሆንዋ አልተጠራጠረም:: ይህም ደስታውን እጥፍ አደረገለት፡፡ ነገር ግን ልጅትዋን የግሉ ሀብት አድርጎ በመቀበልና የደስታው ምንጭ እንድትሆን በማድረጉ በመጠኑም ቢሆን የሕሊና ወቀሣ
ነበረበት::
ይህቺ ልጅ ገና እምቡጥ ናት:: ምንም ነገር አታውቅም:: ሕይወትዋን እንደፈቀደ የሚመራው ዣን ቫልዣ ነው:: ይህንንም ያደረገው ከክፉ ነገር
ላይ እንዳትወድቅ በማሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን ዓይነቱ አስተዳደግ የዓለምን ምንነት ለማወቅ እድል አልሰጣትም:: የራስዋን እድል ራስዋ ልትወስን አልቻለችም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሰውዬው ይህቺን ልጅ እንደ ቦይ ውሃ የመራት ከእርሱ እንዳትሄድ እንጂ ሙሉ በመሉ ለእርስዋ ብሎ አልነበረም፡፡
ይህ ነው የሕሊና ወቀሣ ያስከተለበት::
ከመነኩሴ ትምህርት ቤት ያስገባት እርሱ ነው:: መነኩሲት እንድትሆን የወሰነው እርሱ በመሆኑ ምናልባት ስታድግ በዚህ የተነሣ ልትጠላው ትችላለትች፡ ይህንና ይህን የመሳሰለ አሳቦች ናቸው ገዳሙን ለቅቆ እንዲወጣ
ያደረጉት:: ከዚህ ለመውጣት ከውሳኔ አሳብ ከደረሰ በኋላ አልቆየም::ግቢውን ለቅቆ ለመውጣት ጥሩ አጋጣሚ እየጠበቀ ሳለ ሽማግሌው ፎሽለማ መሞታቸው በዚሁ ሳቢያ ግቢውን ለቅቆ ወጣ፡፡
ከገዳሙ ሲወጣ ለገዳሙ አለቃ የነገራቸው ወንድሙ በመሞታቸውና እንደ እርሳቸውም መሞት የተነሣ መጠነኛ ሀብት ስለወረሰ ሌላ ቦታ ሄዶ መኖር የሚችል መሆኑን ነበር፡፡ ስለዚህ ልጁን ይዞ ያለ ብዙ ድካም ከሌላ
ቦታ ለመኖር የወሰነ መሆኑን ሲነግራቸው አልተቃወሙትም:: ልጅትዋን በማስተማር ገዳሙ ላበረከተው አስተዋጽኦ ለገዳሙ አምስት ሺህ ፍራንክ በስጦታ መልክ ሰጥቶ ነው የወጣው::
ከገዳሙ ሲወጣ የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅና ማንንም ሳያስቸግር
ያቺን ትንሽ ሳጥን እርሱ ራሱ በእጁ ይዞ ነው የወጣው:: የሳጥንዋን ቁልፍ ዘወትር ከእርሱ አይለያትም:: ስለሳጥንዋ ኮዜት ሁልጊዜም ትገረማለች፡፡አንድ ዓይነት የተለየ ጠረን አላት:: ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሳጥንዋን ከራሱ አይለያትም:: ሁልጊዜም የሚያስቀምጣት ከራሱ ክፍል ውስጥ ነው:: ከቦታ ወደ ቦታ በተዘዋወሩ ቀጥር እርስዋን ብቻ ነው አንጠልጥሉ የሚሄደው::
ኮዜት «ይህቺን ሣጥን ቀናሁባት» እያለች አንዳንዴ ብቻዋን ትስቃለች::
ከጊዜ በኋላ ዣን ቫልዣ ወደ ከተማ በወጣ ቁጥር እየተጨነቀ እንጂ
መዝናናትን ከተወ ሰንበት ብሉአል:: ፕሎሜ ጎዳና ላይ ካለው ቤት ውስጥ ከገባ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ከቤት አይወጣም:: ከዚያ ቤት ውስጥ እያለ ስሙ የሚታወቀው ኧልቲስ ፎሽለማ በሚል ስያሜ ነው::
እዚያው ቤት ውስጥ እያለ ሌሉች ሁለት አነስተኛ ቤቶች ከተለያዩ
ሰፈር ተከራይቶ በስሙ ይይዛል:: አልፎ አልፎ ወደ እነዚህ ቤቶች ተራ በተራ አንድ ጊዜ ከአንደኛው በሌላ ጊዜ ደግሞ ከሁለተኛው እየሄደ ወርም ሁለት ወርም ኮዜትን ይዞ ይቀመጣል:: አሮጊትዋን ግን ይዟት አይሄድም፡፡ይህንንም ያደረገው ከፖሊሶች ለመሰወር ነበር፡፡
ከቤት ውስጥ ሲሆኑ ቤቱን የምትመራው ኮዜት ናት ገዳም ውስጥ እያለች ስለቤት አያያዝ ትምህርት ቀስማለች:: ብዙውን ጊዜ ዣን ቫልዣ በጓሮ በኩል ከነበሩት ቤቶች ውስጥ ሲቀመጥ ኮዜት ከትልቁ ቤት ውስጥ
ፎቅ ላይ ነው የምትቀመጠው:: በየቀኑ ዣን ቫልዣ የኮዜትን እጅ እየያዘ ከዚያ ከተንጣለለውና ስአበባ ከአጌጠው ግቢያቸው ውስጥ ይንሸራሽራሉ፡፡
ወደ ከተማ የሚወጠበት ቀን
ውሰን ነው:: እሑድ እሑድ ግን
ወደ ውጭ ወጣ ብለው ይንሸራሸራሉ በዚህ ጊዜ የኮዜትን ቁንጅና ተመልካች እየበዛ መጣ በርግጥ እርሷም ሁሌ የምታስበው ነው ለሽርሽር በወጡ ቁጥር ወንዶች ሰብሰብ ብለው አንዱን አፍጥጣ ስታይ አንድ ሰው ‹‹በእርግጥም ቆንጆ ነሽ የሚላት መሰላት::ትንሽ ተሽኮረመመች:: ያን እለት ማታ ጥሩ እንቅልፍ አልተኛችም፡፡ ከተኛች በኋላ «እውነትም ቆንጆ ነኝ፤ የወንዶች ልብ አሁን እኔን ይመኛል?»
ስትል ብዙ አሰበች:: ገዳም ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የምታውቃቸውን ጓደኞችዋን በማስታወስ መልክዋን ከእነርሱ መልክ ጋር ማነፃፀር ጀመረች::
«እኔ እኮ ከእገሊት አላንስም፡፡ እገሊትም ብትሆን እስከዚህም የምትደነቅ ልጅ አይደለችም፡፡ ውይ እገሊት ግን በጣም ቆንጆ ናት:: እኔን ትበልጠኛለች ብቻ ምንዋ ነው ከእኔ የሚበልጠው?» እያለች ስለውበትዋ ታሰላስል
ጀመር::
አንድ ቀን ከግቢው ውስጥ እየተንሸራሸረች ሳለ አሮጊትዋ ቱሴይ
«ጌታዬ ይህቺ ልጅ እንዴት እየቆነጀች እንደሄደች ልብ ብለዋል?» ብላ ስትናገር ትሰማለች:: አባትዋ ምን መልስ እንደሰጠ ግን አልሰማችም::
የቱሴይ ንግግር ግን ስሜትዋን ነካው:: እየሮጠች ወደ ክፍልዋ ሄደች::
ከመስታወት ፊት ቆማ መልክዋን አየችው:: መስታወት በማየት መልክዋ ካስደነገጣት አንድ ሦስት ወር ያህል አልፎአል፡፡ የመጀመሪያው ቀን ሰው
ሳያያት ትንሽ አልቅሳለች:: የምታየው ራስዋን ሳይሆን የሌላ ሰው መስሎአት ነበር።
በጣም ቆንጆ ለመሆንዋ ለሁለተኛ ጊዜ አረጋገጠች:: መስታወቱና
ቱሴይ ያሉት ነገር ትክክል እንደሆነ አልተጠራጠረችም:: ቅርጽዋ፣ የቆዳዋ ቀለም፣ ፀጉርዋ፣ ዓይንዋ፣ ጥርስዋ፣ አፍንጫዋ ይህ ቀረሽ የምትባል ልጅ አልነበረችም:: ውበትዋ እንደጠዋት ፀሐይ ፊትዋ ላይ በራ፤ ተንጸባረቀ፣ ደመቀ፡፡ ወደ አበባው ቦታ ተመለሰች:፡ ወፎች ስለእርስዋ የሚዘምሩ መሰላት።
ራስዋንም እንደ ንግሥት ለመቁጠር ቃጣች::
ተመልሳ ስትመጣ ዣን ቫልዣ በአያት ጊዜ ልቡ ደነገጠ፡፡ የኮዚት
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ከፕሎሜ ጎዳና ላይ ያለ ቤት
ፕሎሜ ከተባለ ጎዳና ላይ ንብረትነቱ የመንግሥት ባለሥልጣን የሆነ ባለአንድ ፎቅ ቤት ነበር፡፡ ቤቱ ሁለት ክፍል ቤት ከፎቁ ላይ፣ ሁለት ክፍል
ደግሞ ከምድር ቤት ነበረው፡፡ በተጨማሪ እንደ ወጥ ቤት የሚያገለግል ተጨማሪ ክፍል ፎቁ ላይ ነበረው:: ከዋናው ጎዳና ጋር የተያያዘ ትልቅ የውጭ በር ሲኖረው በአበባ ያጌጠ ሰፊ ግቢ አለው:: ከበስተጓሮው እንደ
እቃና ማድቤቶች ሊጠቅሙ የሚችሉ ሌሎች ሦስት ክፍሎች ነበሩ:: በጓሮ በኩል ደግሞ የምሥጢር በር አለው::
ምስጢሩን ለሚያውቅ እንጂ ይህ
በር፣ በር መሆኑ በቀላሉ አይታይም:: ቤቱ ብዙ ጊዜ ሰው አይከራየውም::
በ1829 ዓ.ም አንድ በእድሜ በሰል ያለ ሰው መጥቶ ይህን ቤት
ይከራየዋል፡፡ ሰውዬው ብቻውን አልነበረም:: አንዲት ወጣት አብራው ነበረች፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ወጣትዋ ልጅ ደግሞ ኮዜት ናት፡፡ ቀደም ሲል ዣን ቫልዣ ይረዳት የነበረችው አሮጊት ደግሞ አብራቸው ናት:: ስምዋ ቱሴይ ይባላል:: ዣን ቫልዣ ቤቱን የተከራየው መሴይ ፎሽለማ በሚል ስም ነው::
ዣን ቫልዣ ለረጅም ጊዜ የኖረበትን ገዳም ለቅቆ ከወጣ በኋላ ምን
ተፈጸመ ቢባል ምንም የሆነ ነገር የለም:: እንደሚታወሰው ዣን ቫልዣ ገዳሙ ውስጥ ደስ ብሎት ነበር የሚኖረው:: በየቀኑ፡ ኮዜትን ያገኛታል።በተገናኙ ቁጥር ፍቅራቸው እየጠናና የአባትነት ስሜቱ እየዳበረ ይሄዳል፡፡
ልጅትዋን ፈጣሪ የሰጠው ፀጋ እንደሆነች ከማነ ባሻገር ይህችን ልጅ ከእርሱ ማንም ሊለያት እንደማይችል ገምቷል:: እስከ ሕይወቱ መጨረሻ ከእርሱ የማትለይ ፍጡር ለመሆንዋ አልተጠራጠረም:: ይህም ደስታውን እጥፍ አደረገለት፡፡ ነገር ግን ልጅትዋን የግሉ ሀብት አድርጎ በመቀበልና የደስታው ምንጭ እንድትሆን በማድረጉ በመጠኑም ቢሆን የሕሊና ወቀሣ
ነበረበት::
ይህቺ ልጅ ገና እምቡጥ ናት:: ምንም ነገር አታውቅም:: ሕይወትዋን እንደፈቀደ የሚመራው ዣን ቫልዣ ነው:: ይህንንም ያደረገው ከክፉ ነገር
ላይ እንዳትወድቅ በማሰብ ነበር፡፡ ሆኖም ይህን ዓይነቱ አስተዳደግ የዓለምን ምንነት ለማወቅ እድል አልሰጣትም:: የራስዋን እድል ራስዋ ልትወስን አልቻለችም:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሰውዬው ይህቺን ልጅ እንደ ቦይ ውሃ የመራት ከእርሱ እንዳትሄድ እንጂ ሙሉ በመሉ ለእርስዋ ብሎ አልነበረም፡፡
ይህ ነው የሕሊና ወቀሣ ያስከተለበት::
ከመነኩሴ ትምህርት ቤት ያስገባት እርሱ ነው:: መነኩሲት እንድትሆን የወሰነው እርሱ በመሆኑ ምናልባት ስታድግ በዚህ የተነሣ ልትጠላው ትችላለትች፡ ይህንና ይህን የመሳሰለ አሳቦች ናቸው ገዳሙን ለቅቆ እንዲወጣ
ያደረጉት:: ከዚህ ለመውጣት ከውሳኔ አሳብ ከደረሰ በኋላ አልቆየም::ግቢውን ለቅቆ ለመውጣት ጥሩ አጋጣሚ እየጠበቀ ሳለ ሽማግሌው ፎሽለማ መሞታቸው በዚሁ ሳቢያ ግቢውን ለቅቆ ወጣ፡፡
ከገዳሙ ሲወጣ ለገዳሙ አለቃ የነገራቸው ወንድሙ በመሞታቸውና እንደ እርሳቸውም መሞት የተነሣ መጠነኛ ሀብት ስለወረሰ ሌላ ቦታ ሄዶ መኖር የሚችል መሆኑን ነበር፡፡ ስለዚህ ልጁን ይዞ ያለ ብዙ ድካም ከሌላ
ቦታ ለመኖር የወሰነ መሆኑን ሲነግራቸው አልተቃወሙትም:: ልጅትዋን በማስተማር ገዳሙ ላበረከተው አስተዋጽኦ ለገዳሙ አምስት ሺህ ፍራንክ በስጦታ መልክ ሰጥቶ ነው የወጣው::
ከገዳሙ ሲወጣ የማንንም እርዳታ ሳይጠይቅና ማንንም ሳያስቸግር
ያቺን ትንሽ ሳጥን እርሱ ራሱ በእጁ ይዞ ነው የወጣው:: የሳጥንዋን ቁልፍ ዘወትር ከእርሱ አይለያትም:: ስለሳጥንዋ ኮዜት ሁልጊዜም ትገረማለች፡፡አንድ ዓይነት የተለየ ጠረን አላት:: ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሳጥንዋን ከራሱ አይለያትም:: ሁልጊዜም የሚያስቀምጣት ከራሱ ክፍል ውስጥ ነው:: ከቦታ ወደ ቦታ በተዘዋወሩ ቀጥር እርስዋን ብቻ ነው አንጠልጥሉ የሚሄደው::
ኮዜት «ይህቺን ሣጥን ቀናሁባት» እያለች አንዳንዴ ብቻዋን ትስቃለች::
ከጊዜ በኋላ ዣን ቫልዣ ወደ ከተማ በወጣ ቁጥር እየተጨነቀ እንጂ
መዝናናትን ከተወ ሰንበት ብሉአል:: ፕሎሜ ጎዳና ላይ ካለው ቤት ውስጥ ከገባ ጀምሮ ብዙ ጊዜ ከቤት አይወጣም:: ከዚያ ቤት ውስጥ እያለ ስሙ የሚታወቀው ኧልቲስ ፎሽለማ በሚል ስያሜ ነው::
እዚያው ቤት ውስጥ እያለ ሌሉች ሁለት አነስተኛ ቤቶች ከተለያዩ
ሰፈር ተከራይቶ በስሙ ይይዛል:: አልፎ አልፎ ወደ እነዚህ ቤቶች ተራ በተራ አንድ ጊዜ ከአንደኛው በሌላ ጊዜ ደግሞ ከሁለተኛው እየሄደ ወርም ሁለት ወርም ኮዜትን ይዞ ይቀመጣል:: አሮጊትዋን ግን ይዟት አይሄድም፡፡ይህንንም ያደረገው ከፖሊሶች ለመሰወር ነበር፡፡
ከቤት ውስጥ ሲሆኑ ቤቱን የምትመራው ኮዜት ናት ገዳም ውስጥ እያለች ስለቤት አያያዝ ትምህርት ቀስማለች:: ብዙውን ጊዜ ዣን ቫልዣ በጓሮ በኩል ከነበሩት ቤቶች ውስጥ ሲቀመጥ ኮዜት ከትልቁ ቤት ውስጥ
ፎቅ ላይ ነው የምትቀመጠው:: በየቀኑ ዣን ቫልዣ የኮዜትን እጅ እየያዘ ከዚያ ከተንጣለለውና ስአበባ ከአጌጠው ግቢያቸው ውስጥ ይንሸራሽራሉ፡፡
ወደ ከተማ የሚወጠበት ቀን
ውሰን ነው:: እሑድ እሑድ ግን
ወደ ውጭ ወጣ ብለው ይንሸራሸራሉ በዚህ ጊዜ የኮዜትን ቁንጅና ተመልካች እየበዛ መጣ በርግጥ እርሷም ሁሌ የምታስበው ነው ለሽርሽር በወጡ ቁጥር ወንዶች ሰብሰብ ብለው አንዱን አፍጥጣ ስታይ አንድ ሰው ‹‹በእርግጥም ቆንጆ ነሽ የሚላት መሰላት::ትንሽ ተሽኮረመመች:: ያን እለት ማታ ጥሩ እንቅልፍ አልተኛችም፡፡ ከተኛች በኋላ «እውነትም ቆንጆ ነኝ፤ የወንዶች ልብ አሁን እኔን ይመኛል?»
ስትል ብዙ አሰበች:: ገዳም ውስጥ በነበረችበት ጊዜ የምታውቃቸውን ጓደኞችዋን በማስታወስ መልክዋን ከእነርሱ መልክ ጋር ማነፃፀር ጀመረች::
«እኔ እኮ ከእገሊት አላንስም፡፡ እገሊትም ብትሆን እስከዚህም የምትደነቅ ልጅ አይደለችም፡፡ ውይ እገሊት ግን በጣም ቆንጆ ናት:: እኔን ትበልጠኛለች ብቻ ምንዋ ነው ከእኔ የሚበልጠው?» እያለች ስለውበትዋ ታሰላስል
ጀመር::
አንድ ቀን ከግቢው ውስጥ እየተንሸራሸረች ሳለ አሮጊትዋ ቱሴይ
«ጌታዬ ይህቺ ልጅ እንዴት እየቆነጀች እንደሄደች ልብ ብለዋል?» ብላ ስትናገር ትሰማለች:: አባትዋ ምን መልስ እንደሰጠ ግን አልሰማችም::
የቱሴይ ንግግር ግን ስሜትዋን ነካው:: እየሮጠች ወደ ክፍልዋ ሄደች::
ከመስታወት ፊት ቆማ መልክዋን አየችው:: መስታወት በማየት መልክዋ ካስደነገጣት አንድ ሦስት ወር ያህል አልፎአል፡፡ የመጀመሪያው ቀን ሰው
ሳያያት ትንሽ አልቅሳለች:: የምታየው ራስዋን ሳይሆን የሌላ ሰው መስሎአት ነበር።
በጣም ቆንጆ ለመሆንዋ ለሁለተኛ ጊዜ አረጋገጠች:: መስታወቱና
ቱሴይ ያሉት ነገር ትክክል እንደሆነ አልተጠራጠረችም:: ቅርጽዋ፣ የቆዳዋ ቀለም፣ ፀጉርዋ፣ ዓይንዋ፣ ጥርስዋ፣ አፍንጫዋ ይህ ቀረሽ የምትባል ልጅ አልነበረችም:: ውበትዋ እንደጠዋት ፀሐይ ፊትዋ ላይ በራ፤ ተንጸባረቀ፣ ደመቀ፡፡ ወደ አበባው ቦታ ተመለሰች:፡ ወፎች ስለእርስዋ የሚዘምሩ መሰላት።
ራስዋንም እንደ ንግሥት ለመቁጠር ቃጣች::
ተመልሳ ስትመጣ ዣን ቫልዣ በአያት ጊዜ ልቡ ደነገጠ፡፡ የኮዚት
👍19❤4
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::
አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡
የማን ጥፋት ነው? የማንም::
አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።
አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡
አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::
ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::
ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::
«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::
ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::
ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::
ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡
«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::
አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::
ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::
«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡
«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!
«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡
«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::
«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::
«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!
በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መጨረሻው እንደ አጀማመሩ አልሆነም
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ኮዜት ከሀዘንዋ እያገገመች መጣች:: የጊዜው
መርዘም፣ ወጣትነትዋ፣ የአባትዋ ፍቅርና የአካባቢዋ ማማር ቀስ በቀስ ሀዘንዋን እንድትረሳ ረዱዋት:: ቀን አልፎ ቀን ሲተካ፧ ወር አልፎ ወር ሲተካ የፍቅርዋ ሙላት በየቀኑ በጠብታዎች እየጎደለ ሄደ:: ወላፈኑ በርዶ
ወደ መጥፋት ተቃረበ፡፡ ሆኖም ረመጠ ጨርሶ ስላልጠፋ ማቃጠሉ፣ ማስጨነቁና ማሰቃየቱን ትቶአታል እንጂ ጨርሶ አልተወገደም::
አንድ ቀን በድንገት ማሪየስ ታወሳት:: «ምን!» አለች:: «ደግሞ ከየት መጣ? ረስቼው አልነበረም እንዴ!» በማሪየስ በኩል ደግሞ «ምነው ከመሞቴ በፊት አንድ ጊዜ ብቻ ባየኋት!» የሚልበት ወቅት ነበር፡፡
የማን ጥፋት ነው? የማንም::
አንዳንድ ሰው ከገባበት ወጥመድ በቀላሉ መውጣት አይችልም፡፡
ማሪየስ የዚያ ዓይነት ሰው ነው:: ከደረሰበት ሀዘን እንደ ኮዜት በቀላሉ ሊላቀቅ አልቻለም:: ሀዘን ውስጥ ገብቶ እዚያው ነው ተዘፍቆ የቀረው።
አንድ አጋጣሚ ይከተላል፡፡ በትልቁ በር በኩል ከአንድ ግቢ ውስጥ
አንድ እንደ መቀመጫ የሚያገለግል ጥርብ ድንጋይ ነበር፡፡ እንደ ሴት ጎፈሬ
የተከረከመ የዛፍ አጥር በአጠገቡ ስለነበር ማንም ሰው በመንገድ ሲያልፍ ወደ ውስጥ ማየት አይችልም፡፡ ነገር ግን ከውስጥ ያለ ሰው ከፈለገ እጁን
በአጥሩ ቀዳዳ በማበጀት አሾልኮ በውጭ የሚያልፈውን ሰው ማየትና መጨበጥ ይችላል፡፡
አንድ ቀን ማታ ዣን ቫልዣ ወደ ውጭ ወጥቶ ነበር፡፡ አየሩ ጥሩ
ስለነበር መሸት ሲል ኮሴት ከዚያ ድንጋይ ላይ ተክዛ ቁጭ ብላለች፡፡ የጥንት ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ጊዜው ጨለምለም ብሏል፡፡ የእናትዋ መንፈስ ከዚያ ያለ መሰላት፡፡ ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ ሄደች::
ቀደም ሲል ዝናብ ዘንቦ ስለነበር ሳሩ ያቀዘቅዛል፡፡ «ይህስ ጉንፋን
ያሲዛል ፧ ብቀመጥ ይሻላል» ብላ ወደ ድንጋዩ መቀመጫ ስትመለስ
መቀመጫው ላይ አንድ ነገር አየች:: አንድ እጥፍጥፍ ብላ የተጠቀለለ ነገር ከትንሽ ጠጠር ጋር ተያይዟል:: ከመቀመጫው ተነስታ ስትሄድ ከዚያ
አልነበረም::
ኮዜት ገርሞኣት «ምንድነው እሱ?» ስትል ራስዋን ጠየቀች:: መቼም ሰው ካላስቀመጠው በራሱ ኃይል ሊመጣ እንደማይችል ተረዳች:: ፍርሃት፣ፍርሃት፣ አላት፡፡ ድንጋዩን መንካት አልደፈረችም:: ወደኋላ ሳታይ ቤትዋ ሮጠች፡፡ ቤትዋ ከገባች በኋላ በርና መስኮት ዘጋጋች፡፡ መቀርቀሪያዎቹን
ሁሉ ቀረቀረች:: ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ ‹አባባ ተመልሷል እንዴ?»
ስትል ቱሴይን ጠየቀቻት::
«ኧረ አልተመለሰም» አለቻት::
ክፍሎቹ በሙሉ ተዘግተው እንደሆነና ከቤት ውስጥ ሰው እንዳለ እንድታይ ቱሴይን አዘዘቻት:: አጎንብሳ ከአልጋዋ ስር እንዲሁም ቁም ሣጥንዋን ከፍታ ሰው እንዳለና እንደሌለ አጣራች:: ከተኛች በኋላ ያ ያየችው
ጠጠር ተራራ አክሉ በውስጡ ዋሻ እንዳለበት አለመች::
ጠዋት ፀሐይ ስትወጣና ጨለማ ለብርሃን ቦታዋን ስትለቅ ማታ
እንደዚያ ያስፈራሩን ነገሮች እንደሚያስቁን ይታወቃል:: ኮዜት ስትነቃ ማታ እንደዚያ ያስፈራት ነገር ቅዠት መስሎ ታያት:: ስለምን ነበር የምቃዠው?» ስትል ራስዋን ጠየቀች::
ልብስዋን ለብሳ ወደ አትክልቱ ቦታ ሄደች:: ስትፈራኛ ስትቸር ማታ
ተቀምጣበት ወደነበረው የድንጋይ መቀመጫ ሄደች:: የተጠቀለለው ነገር ከዚያው ቁጭ ብሉአል:: በመጀመሪያ ትንሽ ፈርታ ነበር:: በኋላ ግን ፍርሃቱ ተወገደላት:: ደግሞም በጨለማ የሸሸነወ ነገር በብርሃን እንጓጓለታለንና ምን እንደሆነ ለማየት ቸኩለች፡፡
«አይ ምን አስፈራኝ፤ ፈትቼ ልየዋ» አለች ለራስዋ:: የተጠቀለለውን
ነገር አንስታ ከፈታታችው በኋላ አብሮ ታስሮ የነበረውን ድንጋይ ጣለችው::
አድራሻ ያልተጻፈበትና በውስጠ ወረቀት ያለው እንደ ደብዳቤ ያለ ነገር መሆኑን ተገነዘበች:: ወረቀቱን ከውስጡ ሳታወጣ አገላብጣ አየችው:: አሁን መፍራትዋ ቀርቶ «ከውስጡ ምን አለ» በማለት በመጓጓት ለማወቅ ፈለገች::
ፖስታውን ከፍታ ከውስጡ የነበረውን ወረቀት አወጣች:: በጥሩ የእጅ ጽሑፍ እንደ ጥቅስ ያሉ ነገሮች ተጽፎበታል፡፡ የገጹ ብዛት ከአንድ በላይ ነው:: እያንዳንዱ ገጽ ላይ ቁጥር ተጽፎበታል:: ሆኖም እያንዳንዱ ገጽ ሞልቶ የተጻፈበት ሳይሆን መሐሉ ላይ ብቻ ነው የተጻፈው:: የመጻፊያ ቦታ እያለ ወደ ሚቀጥለው ገጽ ይዞራል::
ፊርማ ወይም ስም ካለበት በሚል በችኮላ ፈለገች፤ ግን አላገኘችም::
ለማነው የተጻፈው? ለራስዋ እንደሆነ ጠረጠረች፡፡ ምክንያቱም እርስዋ ተቀምጣበት ከነበረው ሥፍራ ነው የተገኘው፡፡ ታዲያ ማነው ጸሐፊው?
ግራ ገባት:: በመገላመጥ አካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከርግቦች በስተቀር ምንም ነገር የለም:: ወረቀቱን ማንበብዋን ቀጠለች::
ቀጥሎ የተመለከተው ነበር በወረቀቶቹ ላይ የተጻፈው::
«ዓለም ተጨብጣ አንዲት ትንሽ ነገር ስትሆን፧ አንዲት ትንሽ ነገር
ደግሞ ተነፍታ እግዚአብሔርን ስታክል ፍቅር ትባላለች፡፡ ፍቅር ነፍስን ትመስላለች፤ አፈጣጠራቸው አንድ ነው፡፡ እንደ ነፍስ የመንፈስ ቅዱስ
ብልጭታ ኣለባት፡፡ እንደ ነፍስ ግን አትገድፍም፣ አትነጣጠልም
አትጠፋም፡፡ የእሳት ረመጥ ስትሆን በውስጣችን አለች፤ ዘላለማዊ ናት..ማለቂያና መደምደሚያ የላትም፡፡ ረመጥዋ በምንም ነገር አይጠፋም::
ከአጥንታችን ውስጥ እንኳን ገብታ ስትፋጅ ይሰማናል:: እንዲሁም ከሰማየ ሰማያት ወርዳ፧ ከአካል ውስጥ ዘልቃ ትገባለች፡፡ ሆኖም ስታንፀባርቅ አካላችን ውስጥ በጉልህ እናያታለን፡፡
«ፍቅር! አድናቆት! የሁለት የሚግባቡ አእምሮዎች ፣ የሁለት
የሚወሳሰቡ ልቦች፣ የሁለት አካልን ሰነጣጥቀው የሚገቡ ዓይኖች ያላት ብርሃን! አንቺ ደስታ ወደ እኔ ትመጪያለሽ ወይስ አትመጪም! ፍቅር
ብቸኝነትን ሲያጠቃ አብሮ የሚጓዝ፤ የሚንሸራሽር! የተባረኩ ቀኖች! የሰዎችን እድል፣ የሰዎችን እጣ ፈንታ ለመካፈል መላእክት ከሰማየ ሰማያት ወርደው
በዚህች ምድር ሲኖሩ በሕልሜ ያየኋቸው ነው የመሰለኝ፡፡ አይ ፍቅር!
«ዘላለማዊ ከማድረግ በስተቀር ማንም ከሁለት ከሚዋደዱ ፍጡሮች ደስታ ላይ የሚጨምረው ነገር የለም፡፡ በእርግጥ የፍቅር ዘላለማዊነት
ከፍቅር ዘመን በኋላ የሚታከል ነው:: ግን የፍቅርን መጠን፣ የፍቅርን ግለት ለማሳደግ ከፍቅረኞቹ ከራሳቸው በስተቀር ማንም ሊያስቀረው አይቻለውም፡፡ ፍቅር የሰዎች ፍጹምነት ይታይበታል፡፡
«ከዋክብትን የምናይበት ምክንያት ሁለት ነው:: ይኸውም
ስለሚያብረቀርቁ ወይም ምንነታቸውን ስለማናውቅ! ከጎናችን ግን ከከዋክብት
ይበልጥ ምሥጢሩ ያልታወቀ የላመ፣ የለሰለሰና የሚያንፀባርቅ ፍጡር አለ... ሴት::
«ድንጋይ ከሆንክ ትልቅ ድንጋይ ሁን፤ የዛፍና የቅጠላቅጠል ዘር
ከሆንክ ስሜት፤ ሰው ከሆንክ ደግሞ ፍቅር ይኑርህ::
«ወደ ሽርሽሩ ቦታ ትመጣለች? የለም ጌታዬ! በየሳምንቱ እሑድ ወደ ቤተክርስቲያን ትመጣ የለ? የለም መምጣቱን ትታለች:: አሁን ከዚሁ ቤት ውስጥ ነው የምትኖረው? የለም ለቅቃለች፡፡ አሁን ከየት ሰፈር ገባች?
አድራሻዋ አይታወቅም፡፡ ስትሄድ አልተናገረችም? አልነገረችንም:: ምን ዓይነት የተዳፈነ ጨለማ ነው እባካችሁ የአንድን ነፍስ አድራሻ አለማወቅ!
በፍቅር ምክንያት የምትጨነቅ፣ የምትሰቃይ ነፍስ! አሁንም ውደድ፤ በይበልጥ አፍቅር፡፡ በፍቅር መሞት ማለት በፍቅር መኖር ማለት ነውና፡፡
👍17😱1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::
ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::
ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::
«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?
«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡
ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡
እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::
«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::
«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»
በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::
ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::
የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡
ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::
አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡
ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡
ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::
«ስምህ ማነው?»
«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::
«የአንቺስ?»
«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማምለጥ
ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::
በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል
መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::
ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::
ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::
ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::
«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?
«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡
ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡
እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::
«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::
«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»
በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::
ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::
የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡
ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::
አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡
ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡
ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::
«ስምህ ማነው?»
«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::
«የአንቺስ?»
«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማምለጥ
ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::
በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል
መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::
ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
👍21👏2❤1😁1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መማረክና መረሳሳት
ብረት በማግኔት እንደሚሳብ ፍቅረኛም ባፈቀረው ጠዋት ማታ
ይሳባል፤ ይጉተታል፡፡ ሮሚዮ በዡልየት ፍቅር ተጎትቶ በአትክልት ቦታ እንደ ተንሸራሸረ ሁሉ ማሪየስም ከኮዜት የአትክልት ሥፍራ ለመንሸራሸር ተመላለሰ፡፡ ሆኖም ማሪየስ የሮሚዮን ያህል አልተቸገረም:: ሮሚዮ ከዡልዬት
ግቢ ለመግባት ረጅም ግምብ መዝለል ነበረበት:: ማሪየስ ግን ይህ አላስፈለገውም:: የሽቦ አጥርን በቀላሉ ፈልቅቆ ነበር የሚገባው:: ቀጭን
ስለነበር ሰፊ ክፍት ቦታ አላስፈለገውም::
አካባቢውም ጭር ያለ ስለነበር ሰው ሳያየው በቀላሉ ሊገባ ቻለ፡፡
የሚመጣው ደግሞ ማታ ማታ ነው:: በዚያች በተባረከች ምሽት ከንፈር ለከንፈር ከተገናኙ ወዲህ በእየለቱ ነው የሚመጣው::
በ1832 ዓ.ም የግንቦት ወርን በሙሉ አንድ ቀን እንኳን ሳይጓደል
ማታ ማታ ተመላልሶ ከፍቅረኛው ጋር ተገናኘ:: እነዚህ ሁለት የዋህ
ፍጡሮች እንዳይገናኙ ጨለማ፣ ብርድ፣ ነፋስ አላገዳቸውም::
በየዕለቱ ሲገናኙ ምን ይሠራሉ? ምንም:: አንዱ ሌላውን በማድነቅ
ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ:: የሚረግጡትን መሬት እንደ ተቀደሰ ቦታ ነው የሚቆጥሩት:: ብዙ ጊዜ የሚያወሩት ስለፍቅር ነው:: ማሪየስ የሙት ልጅ
መሆኑን! ስሙ ማሪየስ ፓንትመርሲ እንደሚባልና የሕግ ባለሙያ እንደሆነ ገልጾላታል፡፡ ኑሮውን የሚያሸንፈው ለአሳታሚ ድርጅቶች አንዳንድ ጽሑፍ
እየጻፈ እንደሆነና አባቱ በአገሩ የታወቀ ጀግና እንደነበር ነገራት፡ እንዲሁም ከዲታው አያቱ ጋር መጣላቱንና የአባቱን ሹመት በመውረስ ባሮን እንደሆነም
ገልጾለታል። ባለማዕረግ ስለሆነ ኮዜት ላይ የተለየ ስሜት አላሳደረባትም::ለእርስዋ ምንም ይሁን ምን ማሪየስ ማሪየስ ነው:: በእርስዋም በኩል ገዳም ውስጥ ማደግዋን፣ እናትና አባትዋ መሞታቸውን፣ የእንጀራ አባትዋ ስም። መሴይ ፎሽለማ መሆኑን፣ ይህም ሰው ድሃን የሚወድ እጅግ ደግና ራሱም ምስኪን እንደሆነና እርስዋን ለማስደሰት ሲል ራሱን ረስቶ ያላደረገው ነገር
እንደሌላ ነገረችው፡፡ የእንጀራ አባትዋ ለእርስዋ ሲል ምቾቱን ሁሉ መሰዋቱንም አስረዳችው::
የሚገርመው ማሪየስ ኮዜትን ስላገኘና በምትነግረው ነገር ሁሉ
ስለረካ ሌላው ቀርቶ አንድ ቀን ሌሊት በቀዳዳ ከነቴናድዬ ቤት ውስጥ ያየውን እንኳን ረስቶ አባትዋ ላይ ደርሶ ስለነበረው ትርኢት አልነገራትም::
ሚስተርና ሚስስ ቴናድዬ በአባትዋ ላይ ስላደረሱት በደልና አባትዋ እንዴት አድርጎ ከዚያ ወጥመድ እንዳመለጠ ለጊዜው አልታወሰውም:: ሌላው ቀርቶ ማታ ያደረገውን ጠዋት፣ ጠዋት የሠራውን ማታ ይረሳል፡፡ አንድ
ሰው ቀን ላይ ተገናኝቶ «ቁርስህን ምንድነው የበላኸው?» ብሎ ቢጠይቀው አያስታውስም፡፡ ጆሮውና ሕሊናው በኮዜት ትዝታ ስለተደፈነ የማስታወስ
ችሎታውን ቀንሶበታል፡፡ ከዚህም በላይ ከኮዜት ተለይቶ የሚያሳልፈው ጊዜ ዝም ብሎ የሚያልፍ እንጂ ኑሮን እየኖረ የሚያልፍ ስላልመሰለው በሌላ
ጊዜ የሚፈጽመው ተግባር ሁሉ እርባነቢስ በመሆነ ይረሳዋል:: ለማሪየስ ኑሮ ወይም ሕይወት ማለት ከኮዜት ጋር የሚያሳልፈው ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ ይህም የእውነተኛ ፍቅር ባሕርይ ነው::
ኮዜት በጣም የተዋበች ልጅ ስትሆን ማሪየስ ነፍስዋንም ጭምር ለማየት ነው የሚፈልገው:: የአንድን ነገር ሁለንተና በጉልህ ለማየት
የሚቻለው ዓይን ሲጨፈን ስለሆነ ማሪየስ ዓይኑን ብዙ ጊዜ ይጨፍናል፡፡ ማሪየስና ኮዜት መጨረሻቸው ምን እንደሚሆን አንስተውና ተነጋግረውበት
አያውቁም፡፡ ማንኛውም ነገር እንደአመጣጡ ነው የሚቀበሉት፡-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣን ቫልዣ ምንም አልጠረጠረም፡ኮዜት ዘወትር ደስ ብሉአት ስላየ
ከዚያ ወዲያ የሚፈልገው ነገር አልነበረምና ደስ እያለው ይኖራል፡፡ ኮዜትም ማሪየስን በማግኘትዋ መንፈስዋ ስለረካ ዘወትር የደስታ ምልክት ግንባርዋ ላይ ይነበባል:: በሁለት ፍቅረኞች መካከል መግባባት ካለ አብረው መኖር
ይችላሉ:: በመካከላቸው ሰላም እስካለ ድሬስ የተለየ ጠባይ ስለማይታይባቸው ሦስተኛ ሰው አዲስ ነገር ሊያይባቸው አይችልም:: ጥቂት ጥንቃቄ በማድረግ ከፍቅረኛቸው ጋር መኖር ይችላሉ::
አባትዋ የፈለገውን ለማድረግ ሲፈልግ ተቃውሞ አላሳየችውም፡፡ ዞርዞር ብዬ ልምጣ? እሺ አባዬ:: ዛሬ ከቤት ልዋል መሰለኝ? እንደፈለግህ፡፡
አብረን እናምሽ፡፡ ደስታውን አልችለውም::አባትዋ ዘወትር አራት ሰዓት አካባቢ ይተኛል፡፡
ማሪየስ እንደሆነ ከኮዚት ጋር ለመጫወት የሚመጣው ከአራት ሰዓት በኋላ ነው:: ቀን ቀን
ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ዣን ቫልዣ እንደሆነ የማሪየስ በሕይወት መኖር እንኳን ረስቷል፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ግን «ምነው ኮዜት፤ ከኋላሽ ኖራ ነክቶሻል ፤ ከየት መጣ?» ብሎ ይጠይቃታል፡፡ ያን እለት ማታ ከማሪየስ
ጋር ግድግዳ ተደግፋ ቆማ ኖሮ ልብስዋን ኖራ ነክቶባታል፡፡
አሮጊትዋ ቱሴይ በጊዜ ስለምትተኛ እርስዋም እንደ ዣን ቫልዣ ምንም ነገር አልጠረጠረችም:: ማሪየስ ደፍሮ ከቤትዋ ውስጥ ገብቶ
አያውቅም፡፡ አትክልቱ ውስጥ እንኳን ቢሆን አሳቻ ቦታ ይቀመጣሉ እንጂ ራሳቸውን አያጋልጡም:: ከአንድ ቦታ ከተቀመጡ አይነሱም:: ሁለቱም
አብረው በመሆናቸው ብቻ ረክተው ወሬም ባያወሩ ደንታ የላቸውም::ሌላው ቀርቶ በመንገድ የሚያልፍ እንኳን እንዳያያቸው ይጠነቀቃሉ፡፡
አብረው ተቀምጠው ሳለ ዓይን ለዓይን መተያየት፤ በየደቂቃው እጅ ለእጅ ተያይዞ ሃያ ጊዜ መጨማመቅ ደስታ ይሰጣቸዋል፡፡ በዚያች ሰዓት መብረቅ
ካጠገባቸወ: ቢወርድ እንኳን አይሰሙትም:: ይህን ያህል ነበር
ተመስጦአቸው::
ሆኖም ሁለቱ ፍቅረኞች በዚህ ሁኔታ እንዳሉ አንዳንድ ችግሮች
ደግሞ ፈር ቀድደው እየገቡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ማታ እንደ ለመደው ማሪየስ ወደ ቀጠሮው ቦታ ለመሄድ አቀርቅሮ ይጓዛል:: ከአንድ ኩርባ መንገድ ላይ
ደርሶ ሊጠመዘዝ ሲል ድምፅ ይሰማል::
‹‹ሚስተር ማሪየስ እንደምን አመሸህ!››
ቀና ብሎ ሲያይ ኢፓኒን ናት:: ደንገጥ አለ፡፡ የኮዜት ቤት ካሳየችው እለት ወዲህ ትዝ ብላው ወይም ተያይተው አያውቁም:: አሁን ላገኘው ደስታ ምክንያት ብትሆንም ጨርሶ ረስቷታል:: መርሳት ብቻ ሳይሆን እንደገና መገናኘታቸው አናደደው::
የተደላደለ ፍቅር አንድን ሰው ፍጹም ያደርገዋል ብንል ተሳስተናል:: በስሜት መዋጥ ዝንጉ እንደሚያደርግም መርሳት የለብንም:: በስሜት የተዋጠ ሰው ክፋትንና ደግነትን መለየት ይሳነዋል፡፡ ውለታን፣ የሥራ
ኃላፊነትንና፡ መቃወስ ያለባቸውን ጉዳዮች ሁሉ ሊያስረሳው ይችላል::
ምን! አንቺ ነሽ እንዴ ኢፓኒን?» ሲል ለሰጠችው ሰላምታ በጥያቄ
መልክ መለሰላት::
«ምነው፣ በጣም ተኮሳትረህ ነው የምታነጋግረኝ? የአጠፋሁት ነገር
አለ?»
«የለም» ሲል መለሰላት::
በእርግጥም የያዘባት ቂም አልነበረም:: ደግሞም የሚቀየምበትም ምክንያት አልነበረውም፡፡ ኮዜትን በሚያነጋግርበት አንደበት ኢፓኒንን በጥሞና ማነጋገሩ ስለከበደው ብቻ ነው እንደዚያ የሆነው:: እርሱ ዝም ሲላት
እርስዋ ጮክ ብላ ተናገረች::
«ንገረኝ እስቲ አሁን» ብላ የሚናገረው ነገር እንደጠፋው ሰው ዝም አለች:: ፈገግታ ለማሳየት ሞከረች፡፡ ግን አቃታት፤ እንደገና ለመናገር ሞከረች::
«እና….» ብላ ንግግርዋን እንደገና አቋርጣ አቀርቅራ ቀረች::
«ደህና አምሽ ማሪየስ» ብላ መንገድዋን ቀጠለች::
፡
፡
#ክፍል_አርባ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
መማረክና መረሳሳት
ብረት በማግኔት እንደሚሳብ ፍቅረኛም ባፈቀረው ጠዋት ማታ
ይሳባል፤ ይጉተታል፡፡ ሮሚዮ በዡልየት ፍቅር ተጎትቶ በአትክልት ቦታ እንደ ተንሸራሸረ ሁሉ ማሪየስም ከኮዜት የአትክልት ሥፍራ ለመንሸራሸር ተመላለሰ፡፡ ሆኖም ማሪየስ የሮሚዮን ያህል አልተቸገረም:: ሮሚዮ ከዡልዬት
ግቢ ለመግባት ረጅም ግምብ መዝለል ነበረበት:: ማሪየስ ግን ይህ አላስፈለገውም:: የሽቦ አጥርን በቀላሉ ፈልቅቆ ነበር የሚገባው:: ቀጭን
ስለነበር ሰፊ ክፍት ቦታ አላስፈለገውም::
አካባቢውም ጭር ያለ ስለነበር ሰው ሳያየው በቀላሉ ሊገባ ቻለ፡፡
የሚመጣው ደግሞ ማታ ማታ ነው:: በዚያች በተባረከች ምሽት ከንፈር ለከንፈር ከተገናኙ ወዲህ በእየለቱ ነው የሚመጣው::
በ1832 ዓ.ም የግንቦት ወርን በሙሉ አንድ ቀን እንኳን ሳይጓደል
ማታ ማታ ተመላልሶ ከፍቅረኛው ጋር ተገናኘ:: እነዚህ ሁለት የዋህ
ፍጡሮች እንዳይገናኙ ጨለማ፣ ብርድ፣ ነፋስ አላገዳቸውም::
በየዕለቱ ሲገናኙ ምን ይሠራሉ? ምንም:: አንዱ ሌላውን በማድነቅ
ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ:: የሚረግጡትን መሬት እንደ ተቀደሰ ቦታ ነው የሚቆጥሩት:: ብዙ ጊዜ የሚያወሩት ስለፍቅር ነው:: ማሪየስ የሙት ልጅ
መሆኑን! ስሙ ማሪየስ ፓንትመርሲ እንደሚባልና የሕግ ባለሙያ እንደሆነ ገልጾላታል፡፡ ኑሮውን የሚያሸንፈው ለአሳታሚ ድርጅቶች አንዳንድ ጽሑፍ
እየጻፈ እንደሆነና አባቱ በአገሩ የታወቀ ጀግና እንደነበር ነገራት፡ እንዲሁም ከዲታው አያቱ ጋር መጣላቱንና የአባቱን ሹመት በመውረስ ባሮን እንደሆነም
ገልጾለታል። ባለማዕረግ ስለሆነ ኮዜት ላይ የተለየ ስሜት አላሳደረባትም::ለእርስዋ ምንም ይሁን ምን ማሪየስ ማሪየስ ነው:: በእርስዋም በኩል ገዳም ውስጥ ማደግዋን፣ እናትና አባትዋ መሞታቸውን፣ የእንጀራ አባትዋ ስም። መሴይ ፎሽለማ መሆኑን፣ ይህም ሰው ድሃን የሚወድ እጅግ ደግና ራሱም ምስኪን እንደሆነና እርስዋን ለማስደሰት ሲል ራሱን ረስቶ ያላደረገው ነገር
እንደሌላ ነገረችው፡፡ የእንጀራ አባትዋ ለእርስዋ ሲል ምቾቱን ሁሉ መሰዋቱንም አስረዳችው::
የሚገርመው ማሪየስ ኮዜትን ስላገኘና በምትነግረው ነገር ሁሉ
ስለረካ ሌላው ቀርቶ አንድ ቀን ሌሊት በቀዳዳ ከነቴናድዬ ቤት ውስጥ ያየውን እንኳን ረስቶ አባትዋ ላይ ደርሶ ስለነበረው ትርኢት አልነገራትም::
ሚስተርና ሚስስ ቴናድዬ በአባትዋ ላይ ስላደረሱት በደልና አባትዋ እንዴት አድርጎ ከዚያ ወጥመድ እንዳመለጠ ለጊዜው አልታወሰውም:: ሌላው ቀርቶ ማታ ያደረገውን ጠዋት፣ ጠዋት የሠራውን ማታ ይረሳል፡፡ አንድ
ሰው ቀን ላይ ተገናኝቶ «ቁርስህን ምንድነው የበላኸው?» ብሎ ቢጠይቀው አያስታውስም፡፡ ጆሮውና ሕሊናው በኮዜት ትዝታ ስለተደፈነ የማስታወስ
ችሎታውን ቀንሶበታል፡፡ ከዚህም በላይ ከኮዜት ተለይቶ የሚያሳልፈው ጊዜ ዝም ብሎ የሚያልፍ እንጂ ኑሮን እየኖረ የሚያልፍ ስላልመሰለው በሌላ
ጊዜ የሚፈጽመው ተግባር ሁሉ እርባነቢስ በመሆነ ይረሳዋል:: ለማሪየስ ኑሮ ወይም ሕይወት ማለት ከኮዜት ጋር የሚያሳልፈው ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ ይህም የእውነተኛ ፍቅር ባሕርይ ነው::
ኮዜት በጣም የተዋበች ልጅ ስትሆን ማሪየስ ነፍስዋንም ጭምር ለማየት ነው የሚፈልገው:: የአንድን ነገር ሁለንተና በጉልህ ለማየት
የሚቻለው ዓይን ሲጨፈን ስለሆነ ማሪየስ ዓይኑን ብዙ ጊዜ ይጨፍናል፡፡ ማሪየስና ኮዜት መጨረሻቸው ምን እንደሚሆን አንስተውና ተነጋግረውበት
አያውቁም፡፡ ማንኛውም ነገር እንደአመጣጡ ነው የሚቀበሉት፡-
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣን ቫልዣ ምንም አልጠረጠረም፡ኮዜት ዘወትር ደስ ብሉአት ስላየ
ከዚያ ወዲያ የሚፈልገው ነገር አልነበረምና ደስ እያለው ይኖራል፡፡ ኮዜትም ማሪየስን በማግኘትዋ መንፈስዋ ስለረካ ዘወትር የደስታ ምልክት ግንባርዋ ላይ ይነበባል:: በሁለት ፍቅረኞች መካከል መግባባት ካለ አብረው መኖር
ይችላሉ:: በመካከላቸው ሰላም እስካለ ድሬስ የተለየ ጠባይ ስለማይታይባቸው ሦስተኛ ሰው አዲስ ነገር ሊያይባቸው አይችልም:: ጥቂት ጥንቃቄ በማድረግ ከፍቅረኛቸው ጋር መኖር ይችላሉ::
አባትዋ የፈለገውን ለማድረግ ሲፈልግ ተቃውሞ አላሳየችውም፡፡ ዞርዞር ብዬ ልምጣ? እሺ አባዬ:: ዛሬ ከቤት ልዋል መሰለኝ? እንደፈለግህ፡፡
አብረን እናምሽ፡፡ ደስታውን አልችለውም::አባትዋ ዘወትር አራት ሰዓት አካባቢ ይተኛል፡፡
ማሪየስ እንደሆነ ከኮዚት ጋር ለመጫወት የሚመጣው ከአራት ሰዓት በኋላ ነው:: ቀን ቀን
ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ዣን ቫልዣ እንደሆነ የማሪየስ በሕይወት መኖር እንኳን ረስቷል፡፡ አንድ ቀን ጠዋት ግን «ምነው ኮዜት፤ ከኋላሽ ኖራ ነክቶሻል ፤ ከየት መጣ?» ብሎ ይጠይቃታል፡፡ ያን እለት ማታ ከማሪየስ
ጋር ግድግዳ ተደግፋ ቆማ ኖሮ ልብስዋን ኖራ ነክቶባታል፡፡
አሮጊትዋ ቱሴይ በጊዜ ስለምትተኛ እርስዋም እንደ ዣን ቫልዣ ምንም ነገር አልጠረጠረችም:: ማሪየስ ደፍሮ ከቤትዋ ውስጥ ገብቶ
አያውቅም፡፡ አትክልቱ ውስጥ እንኳን ቢሆን አሳቻ ቦታ ይቀመጣሉ እንጂ ራሳቸውን አያጋልጡም:: ከአንድ ቦታ ከተቀመጡ አይነሱም:: ሁለቱም
አብረው በመሆናቸው ብቻ ረክተው ወሬም ባያወሩ ደንታ የላቸውም::ሌላው ቀርቶ በመንገድ የሚያልፍ እንኳን እንዳያያቸው ይጠነቀቃሉ፡፡
አብረው ተቀምጠው ሳለ ዓይን ለዓይን መተያየት፤ በየደቂቃው እጅ ለእጅ ተያይዞ ሃያ ጊዜ መጨማመቅ ደስታ ይሰጣቸዋል፡፡ በዚያች ሰዓት መብረቅ
ካጠገባቸወ: ቢወርድ እንኳን አይሰሙትም:: ይህን ያህል ነበር
ተመስጦአቸው::
ሆኖም ሁለቱ ፍቅረኞች በዚህ ሁኔታ እንዳሉ አንዳንድ ችግሮች
ደግሞ ፈር ቀድደው እየገቡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ማታ እንደ ለመደው ማሪየስ ወደ ቀጠሮው ቦታ ለመሄድ አቀርቅሮ ይጓዛል:: ከአንድ ኩርባ መንገድ ላይ
ደርሶ ሊጠመዘዝ ሲል ድምፅ ይሰማል::
‹‹ሚስተር ማሪየስ እንደምን አመሸህ!››
ቀና ብሎ ሲያይ ኢፓኒን ናት:: ደንገጥ አለ፡፡ የኮዜት ቤት ካሳየችው እለት ወዲህ ትዝ ብላው ወይም ተያይተው አያውቁም:: አሁን ላገኘው ደስታ ምክንያት ብትሆንም ጨርሶ ረስቷታል:: መርሳት ብቻ ሳይሆን እንደገና መገናኘታቸው አናደደው::
የተደላደለ ፍቅር አንድን ሰው ፍጹም ያደርገዋል ብንል ተሳስተናል:: በስሜት መዋጥ ዝንጉ እንደሚያደርግም መርሳት የለብንም:: በስሜት የተዋጠ ሰው ክፋትንና ደግነትን መለየት ይሳነዋል፡፡ ውለታን፣ የሥራ
ኃላፊነትንና፡ መቃወስ ያለባቸውን ጉዳዮች ሁሉ ሊያስረሳው ይችላል::
ምን! አንቺ ነሽ እንዴ ኢፓኒን?» ሲል ለሰጠችው ሰላምታ በጥያቄ
መልክ መለሰላት::
«ምነው፣ በጣም ተኮሳትረህ ነው የምታነጋግረኝ? የአጠፋሁት ነገር
አለ?»
«የለም» ሲል መለሰላት::
በእርግጥም የያዘባት ቂም አልነበረም:: ደግሞም የሚቀየምበትም ምክንያት አልነበረውም፡፡ ኮዜትን በሚያነጋግርበት አንደበት ኢፓኒንን በጥሞና ማነጋገሩ ስለከበደው ብቻ ነው እንደዚያ የሆነው:: እርሱ ዝም ሲላት
እርስዋ ጮክ ብላ ተናገረች::
«ንገረኝ እስቲ አሁን» ብላ የሚናገረው ነገር እንደጠፋው ሰው ዝም አለች:: ፈገግታ ለማሳየት ሞከረች፡፡ ግን አቃታት፤ እንደገና ለመናገር ሞከረች::
«እና….» ብላ ንግግርዋን እንደገና አቋርጣ አቀርቅራ ቀረች::
«ደህና አምሽ ማሪየስ» ብላ መንገድዋን ቀጠለች::
👍21
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ምን እንደሚያደርጉ ሳይታወቃቸው ከንፈር ለከንፈር ይገናኛሉ፡፡ ዓይናቸው እምባ አቅርሮ አንዱ ሌላው ላይ ማፍጠጥ ሆነ፡፡ ማሪየስና ኮዜትም የፈጸሙት ተግባር ይኸው ነበር፡፡
የማሪየስ አያት በዚህ ጊዜ ዘጠና አንድ ዓመት ሆኖአቸዋል፡፡ አሁንም
ከዚያ ትልቅ ቤታቸው ውስጥ ከሴት ልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት:: በዚህ እድሜያቸው ወገባቸው ሳይጎብጥና ሀዘን ፊታቸውን ሳይሰባብር ቀጥ ብለው
የሚጓዙና ለምሳሌነት ሊቀርቡ የሚችሉ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው::
ሽማግሌው ሠራተኞችን መደብደብና ምርኩዛቸውን ሳይዞ መንቀሳቀስ በተው ጊዜ ልጃቸው «አሁንስ አባቴ በእርግጥ አርጅቷል» እያለች ታስብ
ጀመር፡፡ በሐምሌ ወር የተጀመረው የፈረንሣይ አብዮት መጥፎ ስሜት
አሳድሮባቸዋል፡፡ ቢሆንም ሞራላቸው ብርቱ ስለነበር ለማንኛውም ነገር በቀላሉ አልተበገሩም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን መጎዳታቸው ሳይሰማቸው አልቀረም:: ከአራት ዓመት በኋላ እንኳን አንድ ቀን ማሪየስ ከቤታቸው ተመልሶ ከጫማዬ ሥር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቀኛል የሚል እምነት
ነበራቸው:: ማሪየስ ተመልሶ ከቤት ሳይወጣ እሞታለሁ የሚል ሀሳብ
ከሕሊናቸው ውስጥ ገብቶ አያውቅም:: እንዲያውም በቅርበ ማሪየስ ይመለሳል የሚለው እምነታቸው እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ ይህም ለውለታቢሱ የልጅ ልጃቸው የነበራቸው ፍቅር አጠነከረባቸው::
ይህ ልጅ ሰማይና ምድር ቀሚጨልምበት በክረምት ወራት ነበር ጥሎአቸው የሄደው:: ሽማግሌው በእርሳቸው በኩል ምንም ጥፋት እንደሌለና
ጥፋቱ የማሪየስ እንደሆነ በፍጹም ልቦናቸው ቢያምኑም ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ግን አልተቀነሰም፡፡ በመጨረሻ ወደ ሞት መቃረባቸው ሲታወሳቸው
ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ያይላል፡፡ ጥርሳቸው መርገፍ ጀምሯል:: ይህም ሀዘናቸውን ከፍ አደረገው::
አንድ ቀን ጉልበታቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን በከፊል ጨፍነው ቁጭ ይላሉ፡፡ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ከፊታቸው ላይ ይነበባል:: ሴት ልጃቸው ጥያቄ ጠየቀቻቸው:
"አባባ፣ አሁንም ልጁን እንደተቀየሙት ነው?»
ይህን ካለች በኋላ ለመቀጠል ስላልደፈረች ዝም አለች::
"ማንን ነው የምትዪው?» ሲሉ ጠየቅዋት::
«ያንን ምስኪን ማሪየስ፡፡»
የሽማግሌ ጭንቅላታቸውን ቀና አደረጉ:: ያንን የተሸበሸበወን
ክርናቸውን ከጠረጴዛ ላይ በማሳረፍ አገጫቸውን ደግፈው ያዙ፡፡ በጣም በተናደደና በተቆጣ አንደበት ተናገሩ፡፡
«ምስኪን ማሪየስ አልሽ? የማይረባ! እርሱ ብሎ ምስኪን፤ አጉራሹን የሚነክስ! የእኛ እልኸኛ! ልስቢስ፣ እንኳን ልብ ነፍስ የለውም::»
እምባ ያቀረረውን ዓይናቸው ልጃቸው እንዳታይ ከነበሩበት ፊታቸውን በማዞር ተነስተው ሄዱ:: ከሦስት ቀን በኋላ በዝምታ አራት ሰዓት ሙሉ ከአንድ ሥፍራ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሽማግሌ ልጃቸውን በመገሰጽ ይናገራሉ::
«ስለዚያ ልጅ ሁለተኛ እንዳታነሽብኝ ብዬ አልነበረም?»
በዚያው ሰሞን መሴይ ጊልኖርማንድ እሳት እየሞቁ አምሽተው ስለደከማቸው በጊዜ ልጃቸውን ደህና እደሪ ብለው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሄዱ:: ልጃቸው ከሚቀጥለው ክፍል ውስጥ በሩን ክፍት አድርጋ ልብስ እየሰፋች ነበር:: ሽማግሌው እሳት ይሞቁ የነበረው ብቻቸውን ሲሆን
መጽሐፍ ለስሙ በእጃቸው ይዘው ነበር እንጂ አያነቡትም::
እሳት እየሞቀ ሳለ የልጅ ልጃቸው ማሪየስን አስታወሱት:: አሁንም
ቢሆን ውስጥ ውስጡን ይናፍቃቸዋል:: ሊታረቁት ፈለጉ፡፡ ግን ልባቸው ውስጥ የገነነው ኩራትና እልህ መንገዱን ዘጋባቸው:: እንዲያውም ከነአካቴው የመታረቅ አሳብ ኅሊናቸው ውስጥ ስለገባ መላ ሰውነታቸውን አንገሸገሸው::
«ምን?» ሲሉ ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ ከአንገታቸው ቀና አሉ:: ከቤት
ውስጥ የገባ ስለመሰላቸው ተንገሸገሹ:: «ከዚህ ቤት ውስጥ ተመልሶ አይገባም» ሲሉ ለራሳቸው ቃል ገቡ:: ያ መላጣ ጭንቅላታቸው ነገር ስለከበደው ከደረታቸው ላይ ዘንበል ብሎ የወደቁ መሰላቸው:: ቀና ብለው
ከግድግዳ ላይ ከተሰቀለው ስእል ላይ አፈጠጡ:: በአሳብ ተውጠው ሳለ ባስክ የተባለ የቤት አሽከራቸው ይገባል፡፡
«ጌታዬ ማሪየስን ያነጋግሩታል?» ሲል ጠየቃቸው:: ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ:: ከአሳባቸው ባንነው ሲነቁ በጣም
ካመደንገጣቸው የተነሳ ጀርባቻው ቀዘቀዛቸው::
‹‹ምን አልክ?» ማሪየስን ነው ያልከው?
«እኔ እንጃ» ሲል ባስክ እየፈራ መልስ ሰጠ፡፡ «እኔ እንኳን በዓይኔ
አላየሁትም:: ሠራተኛዋ ናት የነገረችኝ፡፡ ውጭ ግን አንድ ወጣት መቆሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ማሪየስ ሊሆን ይችላል፡፡»
«ግባ ግባ ግባ በለው» አሉ እየተንተባተቡ፡፡ ልባቸው እንደከበሮ እየመታ ዓይናቸውን በር ላይ ተክለው ቀሩ፡፡ በሩ ተከፈተ:: አንድ ወጣት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ማሪየስ ነበር፡፡
«ገባ በል እንጂ» በማለት እንዲጋበዝ የሚጠብቅ ይመስል ማሪየስ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ ጊዜው ጨልሞ ስለነበር የለበሰው አዳፋ ልብስ መቆሸሹ ብዙም አያስታውቅም፡፡ በሀዘን የተጨማለቀው ፊቱ ምንም እንኳን
ፀጥታ ቢሰፍንበትም መከፋቱን በግልጽ ያሳያል::
መሴይ ጊልኖርማንድ በደስታና በአድናቆት ልቡ እንደተነካ ሰው
ለጥቂት ጊዜ ዝም በማለት ሰማይ ሰማዩን አዩ፡፡ ማሪየስ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሠርቀው አዩት::
በመጨረሻ! ከአራት ዓመት በኋላ! ደስታ አንደበታቸውን ዘግቶ ሽባ
አደረጋቸው:: ባለፉት አራት ዓመታት እንዲያው ሲያስቡት ቆንጆ፣ ረጋ ያለና ምራቁን የዋጠ የጨዋ ልጅ እንደሚሆን ገምተዋል:: ቢመለስ ልባቸው |
በደስታ ፈክቶና ስሜታቸው በሕሊና ዕረፍት ረክቶ እጆቻቸውን ዘርግተው እንደሚቀበሉት ልቦናቸው ተመኝቶ እንደነበር ልቦናቸው ቢያውቁም ያ ሰዓት ሊመጣ ሳያወቁት የማይሆን ቃል አንደበታቸው ውስጥ ይገባል።
«ለምንድነው የመጣኸው?»
ማሪየስ ሀፍረት እየተሰማው መለሰ፡፡
«ጌቶች...»
መሴይ ጊልኖርማንድ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ቢያቅፉት ደስ ባላቸው፤ ግን ማሪየስ አስቀይሞአቸዋል፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውም ቢሆኑ
በወሰዱት እርምጃ ቅር መሰኘታቸው አልቀረም:: ማሪየስ ቢያስቀይማቸውም መታገስ እንደነበረባቸው ያውቃሉ፡፡ ደግና እልኸኛ ሰው የልቡን ደግነት
በእልህና በኃይለ ቃል እየሸፈነ ወስጥ ውስጡን ይሰቃያል:: ምሬቱ ትዝ ብሉአቸው እንዲናገር እድል ሳይሰጡት ጣልቃ ገቡበት::
‹‹ንገረኝ እኮ፣ ለምንድነው የመጣኸው?»
ጉልበቴን ለመሳም ወይም አቅፈህ ጉንጩን በመሳም ይቅርታ ለመጠየቅ ካልሆነ ለምንድነው የመጣኸው ማለታቸው ነበር፡፡ ማሪየስ አያቱን አተኩር
ሲመለከታቸው ሀሞታቸው መፍሰሱን ተገነዘበ፡፡
ሽማግሌው አሁንም በኃይለ ቃል አቋረጡት::
«ይቅርታ ለመጠየቅ ነው የመጣኸው? ተጸጽተህ ነው?»
ወደ እርሳቸው እንዲመለስ በር መክፈታቸው ነበር፡፡ እጁን የሚሰጥና የሚርበተበት መሰላቸው:: እውነትም ማሪየስ በድንጋጤ ሰውነቱ ተርበተበተ፡፡
ዓይኑን ወደ መሬት ሰበረ፡፡ ቢሆንም በድፍረት መልስ ሰጠ፡፡
«የለም ጌቶች::»
«እና ምንድነው የምትፈልገው?» ሲሉ ሽማግሌው ንዴትና ምሬት
እየተናነቃቸው ተናገሩ፡፡ «አሁን ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው?»
ማሪየስ ሁለት እጆቹን በኃይል በመጨበጥ አጋጫቸው አንድ
እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡
እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አባባ ይዘኑልኝ::»
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ምን እንደሚያደርጉ ሳይታወቃቸው ከንፈር ለከንፈር ይገናኛሉ፡፡ ዓይናቸው እምባ አቅርሮ አንዱ ሌላው ላይ ማፍጠጥ ሆነ፡፡ ማሪየስና ኮዜትም የፈጸሙት ተግባር ይኸው ነበር፡፡
የማሪየስ አያት በዚህ ጊዜ ዘጠና አንድ ዓመት ሆኖአቸዋል፡፡ አሁንም
ከዚያ ትልቅ ቤታቸው ውስጥ ከሴት ልጃቸው ጋር ነው የሚኖሩት:: በዚህ እድሜያቸው ወገባቸው ሳይጎብጥና ሀዘን ፊታቸውን ሳይሰባብር ቀጥ ብለው
የሚጓዙና ለምሳሌነት ሊቀርቡ የሚችሉ የእድሜ ባለፀጋ ናቸው::
ሽማግሌው ሠራተኞችን መደብደብና ምርኩዛቸውን ሳይዞ መንቀሳቀስ በተው ጊዜ ልጃቸው «አሁንስ አባቴ በእርግጥ አርጅቷል» እያለች ታስብ
ጀመር፡፡ በሐምሌ ወር የተጀመረው የፈረንሣይ አብዮት መጥፎ ስሜት
አሳድሮባቸዋል፡፡ ቢሆንም ሞራላቸው ብርቱ ስለነበር ለማንኛውም ነገር በቀላሉ አልተበገሩም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ውስጡን መጎዳታቸው ሳይሰማቸው አልቀረም:: ከአራት ዓመት በኋላ እንኳን አንድ ቀን ማሪየስ ከቤታቸው ተመልሶ ከጫማዬ ሥር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቀኛል የሚል እምነት
ነበራቸው:: ማሪየስ ተመልሶ ከቤት ሳይወጣ እሞታለሁ የሚል ሀሳብ
ከሕሊናቸው ውስጥ ገብቶ አያውቅም:: እንዲያውም በቅርበ ማሪየስ ይመለሳል የሚለው እምነታቸው እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ ይህም ለውለታቢሱ የልጅ ልጃቸው የነበራቸው ፍቅር አጠነከረባቸው::
ይህ ልጅ ሰማይና ምድር ቀሚጨልምበት በክረምት ወራት ነበር ጥሎአቸው የሄደው:: ሽማግሌው በእርሳቸው በኩል ምንም ጥፋት እንደሌለና
ጥፋቱ የማሪየስ እንደሆነ በፍጹም ልቦናቸው ቢያምኑም ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ግን አልተቀነሰም፡፡ በመጨረሻ ወደ ሞት መቃረባቸው ሲታወሳቸው
ለልጁ የነበራቸው ፍቅር ያይላል፡፡ ጥርሳቸው መርገፍ ጀምሯል:: ይህም ሀዘናቸውን ከፍ አደረገው::
አንድ ቀን ጉልበታቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን በከፊል ጨፍነው ቁጭ ይላሉ፡፡ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ከፊታቸው ላይ ይነበባል:: ሴት ልጃቸው ጥያቄ ጠየቀቻቸው:
"አባባ፣ አሁንም ልጁን እንደተቀየሙት ነው?»
ይህን ካለች በኋላ ለመቀጠል ስላልደፈረች ዝም አለች::
"ማንን ነው የምትዪው?» ሲሉ ጠየቅዋት::
«ያንን ምስኪን ማሪየስ፡፡»
የሽማግሌ ጭንቅላታቸውን ቀና አደረጉ:: ያንን የተሸበሸበወን
ክርናቸውን ከጠረጴዛ ላይ በማሳረፍ አገጫቸውን ደግፈው ያዙ፡፡ በጣም በተናደደና በተቆጣ አንደበት ተናገሩ፡፡
«ምስኪን ማሪየስ አልሽ? የማይረባ! እርሱ ብሎ ምስኪን፤ አጉራሹን የሚነክስ! የእኛ እልኸኛ! ልስቢስ፣ እንኳን ልብ ነፍስ የለውም::»
እምባ ያቀረረውን ዓይናቸው ልጃቸው እንዳታይ ከነበሩበት ፊታቸውን በማዞር ተነስተው ሄዱ:: ከሦስት ቀን በኋላ በዝምታ አራት ሰዓት ሙሉ ከአንድ ሥፍራ ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ ሽማግሌ ልጃቸውን በመገሰጽ ይናገራሉ::
«ስለዚያ ልጅ ሁለተኛ እንዳታነሽብኝ ብዬ አልነበረም?»
በዚያው ሰሞን መሴይ ጊልኖርማንድ እሳት እየሞቁ አምሽተው ስለደከማቸው በጊዜ ልጃቸውን ደህና እደሪ ብለው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሄዱ:: ልጃቸው ከሚቀጥለው ክፍል ውስጥ በሩን ክፍት አድርጋ ልብስ እየሰፋች ነበር:: ሽማግሌው እሳት ይሞቁ የነበረው ብቻቸውን ሲሆን
መጽሐፍ ለስሙ በእጃቸው ይዘው ነበር እንጂ አያነቡትም::
እሳት እየሞቀ ሳለ የልጅ ልጃቸው ማሪየስን አስታወሱት:: አሁንም
ቢሆን ውስጥ ውስጡን ይናፍቃቸዋል:: ሊታረቁት ፈለጉ፡፡ ግን ልባቸው ውስጥ የገነነው ኩራትና እልህ መንገዱን ዘጋባቸው:: እንዲያውም ከነአካቴው የመታረቅ አሳብ ኅሊናቸው ውስጥ ስለገባ መላ ሰውነታቸውን አንገሸገሸው::
«ምን?» ሲሉ ራሳቸውን ጠየቁ፡፡ ከአንገታቸው ቀና አሉ:: ከቤት
ውስጥ የገባ ስለመሰላቸው ተንገሸገሹ:: «ከዚህ ቤት ውስጥ ተመልሶ አይገባም» ሲሉ ለራሳቸው ቃል ገቡ:: ያ መላጣ ጭንቅላታቸው ነገር ስለከበደው ከደረታቸው ላይ ዘንበል ብሎ የወደቁ መሰላቸው:: ቀና ብለው
ከግድግዳ ላይ ከተሰቀለው ስእል ላይ አፈጠጡ:: በአሳብ ተውጠው ሳለ ባስክ የተባለ የቤት አሽከራቸው ይገባል፡፡
«ጌታዬ ማሪየስን ያነጋግሩታል?» ሲል ጠየቃቸው:: ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ:: ከአሳባቸው ባንነው ሲነቁ በጣም
ካመደንገጣቸው የተነሳ ጀርባቻው ቀዘቀዛቸው::
‹‹ምን አልክ?» ማሪየስን ነው ያልከው?
«እኔ እንጃ» ሲል ባስክ እየፈራ መልስ ሰጠ፡፡ «እኔ እንኳን በዓይኔ
አላየሁትም:: ሠራተኛዋ ናት የነገረችኝ፡፡ ውጭ ግን አንድ ወጣት መቆሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ማሪየስ ሊሆን ይችላል፡፡»
«ግባ ግባ ግባ በለው» አሉ እየተንተባተቡ፡፡ ልባቸው እንደከበሮ እየመታ ዓይናቸውን በር ላይ ተክለው ቀሩ፡፡ በሩ ተከፈተ:: አንድ ወጣት በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ማሪየስ ነበር፡፡
«ገባ በል እንጂ» በማለት እንዲጋበዝ የሚጠብቅ ይመስል ማሪየስ ከበሩ አጠገብ ቆም አለ፡፡ ጊዜው ጨልሞ ስለነበር የለበሰው አዳፋ ልብስ መቆሸሹ ብዙም አያስታውቅም፡፡ በሀዘን የተጨማለቀው ፊቱ ምንም እንኳን
ፀጥታ ቢሰፍንበትም መከፋቱን በግልጽ ያሳያል::
መሴይ ጊልኖርማንድ በደስታና በአድናቆት ልቡ እንደተነካ ሰው
ለጥቂት ጊዜ ዝም በማለት ሰማይ ሰማዩን አዩ፡፡ ማሪየስ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሠርቀው አዩት::
በመጨረሻ! ከአራት ዓመት በኋላ! ደስታ አንደበታቸውን ዘግቶ ሽባ
አደረጋቸው:: ባለፉት አራት ዓመታት እንዲያው ሲያስቡት ቆንጆ፣ ረጋ ያለና ምራቁን የዋጠ የጨዋ ልጅ እንደሚሆን ገምተዋል:: ቢመለስ ልባቸው |
በደስታ ፈክቶና ስሜታቸው በሕሊና ዕረፍት ረክቶ እጆቻቸውን ዘርግተው እንደሚቀበሉት ልቦናቸው ተመኝቶ እንደነበር ልቦናቸው ቢያውቁም ያ ሰዓት ሊመጣ ሳያወቁት የማይሆን ቃል አንደበታቸው ውስጥ ይገባል።
«ለምንድነው የመጣኸው?»
ማሪየስ ሀፍረት እየተሰማው መለሰ፡፡
«ጌቶች...»
መሴይ ጊልኖርማንድ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ቢያቅፉት ደስ ባላቸው፤ ግን ማሪየስ አስቀይሞአቸዋል፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውም ቢሆኑ
በወሰዱት እርምጃ ቅር መሰኘታቸው አልቀረም:: ማሪየስ ቢያስቀይማቸውም መታገስ እንደነበረባቸው ያውቃሉ፡፡ ደግና እልኸኛ ሰው የልቡን ደግነት
በእልህና በኃይለ ቃል እየሸፈነ ወስጥ ውስጡን ይሰቃያል:: ምሬቱ ትዝ ብሉአቸው እንዲናገር እድል ሳይሰጡት ጣልቃ ገቡበት::
‹‹ንገረኝ እኮ፣ ለምንድነው የመጣኸው?»
ጉልበቴን ለመሳም ወይም አቅፈህ ጉንጩን በመሳም ይቅርታ ለመጠየቅ ካልሆነ ለምንድነው የመጣኸው ማለታቸው ነበር፡፡ ማሪየስ አያቱን አተኩር
ሲመለከታቸው ሀሞታቸው መፍሰሱን ተገነዘበ፡፡
ሽማግሌው አሁንም በኃይለ ቃል አቋረጡት::
«ይቅርታ ለመጠየቅ ነው የመጣኸው? ተጸጽተህ ነው?»
ወደ እርሳቸው እንዲመለስ በር መክፈታቸው ነበር፡፡ እጁን የሚሰጥና የሚርበተበት መሰላቸው:: እውነትም ማሪየስ በድንጋጤ ሰውነቱ ተርበተበተ፡፡
ዓይኑን ወደ መሬት ሰበረ፡፡ ቢሆንም በድፍረት መልስ ሰጠ፡፡
«የለም ጌቶች::»
«እና ምንድነው የምትፈልገው?» ሲሉ ሽማግሌው ንዴትና ምሬት
እየተናነቃቸው ተናገሩ፡፡ «አሁን ከእኔ የምትፈልገው ምንድነው?»
ማሪየስ ሁለት እጆቹን በኃይል በመጨበጥ አጋጫቸው አንድ
እርምጃ ወደፊት ተራመደ፡፡
እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አባባ ይዘኑልኝ::»
👍18🥰1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ወዴት ነው የሚሄዱት?
ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::
እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::
ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡
ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::
ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።
ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።
ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::
ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡
«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::
በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡
ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡
ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡
ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»
ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ወዴት ነው የሚሄዱት?
ያን እለት ከቀኑ ወደ አሥር ሰዓት ገደማ ዣን ቫልዣ ብቸኝነት
ተሰምቶት ብቻውን ተቀምጧል፡፡ ኮዜትን ካየ ስለእርስዋ ብዙ አይጨነቅም፡፡በአንድ ወቅት ገጥሞት የነበረው መጥፎ አጋጣሚ እየተረሳው ሄዷል፡፡
ነገር ግን ከአንድ ወይም ከሁለት ሣምንት በፊት የገጠመው ነገር በጣም እያሳሰበው ሄዶአል:: አንድ ቀን አንድ አውራ ጉዳና ላይ ሲንሸራሸር ቴናድዬን ያየዋል:: የዚህ ክፉ ሰው ከዚያ በነፃ መለቀቅ እጅግ አደገኛ
መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ይህም በጣም አስጨነቀው:: ከዚህም በላይ የፓሪስ ከተማ ሰላም ራቀው:: የፖለቲካ ብጥብጥ እያየለ መጣ፡፡ በዚህም የተነሳ ጸጥታ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ክትትላቸውን አጠናከሩ፡፡ ዣን ቫልዣ በክትትል መጠናከር ሰበብ የሚያዝ ስለመሰለው በጣም ፈራ:: ዣን ቫልዣ ከሚፈለጉት
ሰዎች አንዱ እንደሆነ ልቡ ያውቃል:: ስለዚህ በአስቸኳይ ከፓሪስ መውጣት ነበረበት:: ከፓሪስ ከተማ ብቻ ሳይሆን ከፈረንሳይ መውጣት እንደሚሻል
አመነ:: ከፈረንሣይ አገር ከሄደ ወደ እንግሊዝ አገር መሄዱን ይመርጣል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከፈረንሣይ እንደሚወጡ ለኮዜት የነገራት በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ የቴናድዬ፣ የፖሊስ ክትትል፣ የጉዞውና ፓስፖርት የማውጣቱ
ጉዳይ በጣም አስጨነቀው::
እነዚህ ነገሮች አስጨንቀውት ሳለ ያን እለት በቀን ግቢው ውስጥ
ሲንሸራሸር ከቤቱ ግድግዳ ላይ «ደ ፣ ላ፣ ቤራሪ ጉዳና የቤት ቁጥር 16» የሚል ጽሑፍ በምስማር ተጽፎ ያያል::
ጽሑፉ በቅርቡ ለመጻፉ ያስታውቃል:: ምናልባትም ጽሑፉ ከተጻፈ ቢበዛ አንድ ቀን ውሎ ይደር እንጂ ከዚያ እንደማይበልጥ ይገምታል:: ጽሑፉ ማን ይላል? የሰው አድራሻ ነው? አንድ ሰው ለማመልከት የተጻፈ ይሆን? ለዣን ቫልዣ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው? ምንም ይሁን ምን አንድ
ሰው ግቢውን ደፍሮአል፡፡
ይህን እያሰላሰለ ሰው በአካባቢው ለመኖሩ በጥላው አወቀ፡፡ ሰውዬው ድንገት ይቆማል። ዞር ብዬ ልይ በማለት ሲያስብ የተጠቀለለ ወረቀት
ከእግሩ ሥር ይወድቃል የወረቀታ አወዳደቅ ከላይ ወደታች እንጂ ከሩቅ በጎን የወረወሩት አይመስል
ወረቀቱን አንስቶ ዘረጋው «አስወግድ»የሚል ቃል በትልልቅ ጽሑፍ በእርሳስ ተጽፎ አነበበ::
ዣን ቫልዣ ዞር ዞር አለ፡፡ በዚያ አካባቢ ሰው አልነበረም፡፡ ግን
ግራጫ መልክ ያለው ሸሚዝና የወይን ጠጅ ቀለም ያለው ሰሪ የታጠቀ ልጅ አይሉት ትልቅ ሰው በአጥሩ ዘልሎ ወደ ዋናው ጎዳና ሲወጣ በሩቁ ተመለከተ።
ዣን ቫልዣ ቶሎ ብሎ ወደ ቤቱ ገባ። ከከባድ ጭንቀት ላይ ወደቀ።
ማሪየስ ከመሴይ ጊልኖርማንድ ቤት ከወጣ ቆይቷል:: በታላቅ ተስፋ የገባው ሰውዬ ከቤቱ ሲወጣ ከመጠን በላይ ተስፋ ቆርጦ ነው:: መከራና ስቃይ ያስጨነቀው ሰው እንደሚያደርገው ሁሉ እርሱም
በአሳብ ተውጦ እያቀረቀረ ነው የሚጓዘው:: ጭንቅላቱ ባዶውን ስለቀረ የሚያስበው ነገር አልነበረውም:: ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ከጓደኛው ከኩርፌይራክ ቤት ደረሰ፡፡ ከነልብሱ ራሱን ከአልጋው ላይ ወረወረ፡፡
እስኪነጋ እንቅልፍ አልወሰደውም:: ፀሐይ እንደወጣ እንቅልፍ ወስዶት ኖሮ ክፉኛ አቃዠው::
ቅዠቱ ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ዓይኑን ገልጦ ሲያይ ከቤቱ ውስጥ
የነበሩት አራቱም ጓደኞቹ ለመሄድ ተዘጋጅተዋል፡፡
«ከጄኔራል ላማርክ ቀብር ትገኛለህ?» ሲል ጓደኛው ኩርፌይራክ ጠየቀው::
በቻይና ቋንቋ የሚያናግረው መሰለው:: ማሪየስ ጓደኞቹ ከቤት ከወጡ ጥቂት ቆይቶ ነው የወጣው፡፡ ዣቬር ከሰጠው ሽጉጥ አንዱን ኪሱ ውስጥ
አደረገ፡፡ ሽጉጡ ጥይት እንደጕረሰ ነው፡፡ ምን አስቦ ሽጉጡን እንደያዘ
ለማወቅ ያስቸግራል፡፡ የት እንደሚሄድ ሳያውቅ ቀኑን ሙሉ ከወዲያ ወዲህ ሲንቀዋለል
ዋለ፡፡ አንዳንዴ ዝናብ ቢያካፋም እርሱ አልተሰማውም:: ጦሙን እንዳያድር ለእራቱ የሚሆን ዳቦ ገዝቶ ኪሱ ውስጥ አደረገው፡፡ ግን ኪሱ ውስጥ እንዳለ ረስቶት ሳይበላው አደረ፡፡ ጊዜው ቶሎ አልመሽ ስላለው በጣም ተቁነጠነጠ፡፡ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ከኮዜት ጋር ቀጠሮ ስለነበረው ያቺን ሰዓት በጉጉት ይጠብቃል፡፡ ከተማው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲዞር በአሳብ ጭልጥ ይላል፡፡
ከአሳቡ ሲነቃ የተኩስ ድምፅ ስማ፡፡ «ውጊያ ቀጥለዋል ማለት ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ መሽቶ ሦስት ሰዓት ሲቃረብ ወደ ቀጠሮው ቦታ ሄደ፡፡ ኮዜትን ሳያይ
ሁለት ቀን ስላለፈ በጣም ናፍቆአታል:: ሰዓቱ በመድረሱ በጣም ደስ አለው፡፡ የምንጓጓለት ነገር ልብን ያስጨንቃል እንጂ ቶሎ ስለማይደርስ ደቂቃው እንደ ዓመት ይረዝማል፡፡
ማሪየስ በለመደው ቀዳዳ ከግቢው ውስጥ ገባ፡፡ ኮዜት በሌላ ጊዜ ከምትጠብቀው ሥፍራ የለችም፡፡ ምናልባት ከቤቱ አካባቢ ትጠብቀኝ ይሆናል ብሎ ወደዚያ አመራ:: ከዚያም አልነበረችም:: አንገቱን ቀና አድርጎ ሲያይ
የኮዜት መኝታ ቤት መስኮት ተዘግቷል፡፡ አካባቢው በጣም ጭር ብሏል፡፡ በፍቅር ያበደው፣ የነደደው፣ የተቃጠለውና የሰከረው ወጣት ከፍቅረኛው
መኝታ ቤት መስኮት ላይ አፈጠጠ፡፡ ከአሁን አሁን ተከፍቶ «ኮዜትዬ ብቅ ትላለች» ሲል አወጣ፤ አወረደ፡፡ ግን መስኮቱ እንደተዘጋ ቀረ፡፡ በጨለማ
ለማየት እስከቻለ ድረስ በዓይኑ አካባቢውን ቃኘ:: ማንም የለም:: ድንገት አባትዋ ብቅ ያለ እንደሆነ ‹‹ምን ትፈልጋለህ?» ብሎ ያፈጥብኛል በማለት ሳይፈራ ቤቱን ዞረው:: በመጨረሻ አላስችል ብሎት «ኮዜት» እያለ ደጋግሞ
ተጣራ:: መልስ አላገኘም:: አሁንም ደገመና ተጣራ:: መልስ የለም:: ቤቱ ውስጥ ሰው እንደሌለ አወቀ፡፡
ቤቱን ተስፋ በቆረጠ ዓይን አየው፡፡ ከመቃብር ቤት ይበልጥ ጭር
ብሎአል፡፡ ብዙ የደስታ ምሽቶችን ወዳሳለፈበት የድንጋይ መቀመጫ ሄደ:: ልቡ እየከበደው ከመቀመጫው ላይ ቁጭ አለ፡፡ ለኮዜት ያለውን ፍቅር
እያሰላሰለ ኮዜት ከሄደች ከመሞት በስተቀር ሌላ የተሻለ ምርጫ እንደሌለው አመነ፡፡
ከአጥር ውጭ ድንገት ድምፅ ሰማ
«መሴይ ማሪየስ!»
ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡
‹‹ማነህ?» ሲል ተጣራ
«መሴይ ማሪየስ፣ አንተ ነህ?››
«አዎን፡፡»
«መሴይ ማሪየስ» አለ ድምፁ፣ «ጓደኞችህ ባሪኬድ ከተባለ ሥፍራ ይጠብቁሃል፡፡»
ድምፁ እንግዳ የሆነ ድምፅ አልነበረም፡፡ የኢፓኒንን ድምፅ ይመስላል፡፡ ቶሎ ብሎ ወደ አጥሩ ሄደና በቀዳዳ አየ:: አንድ ወጣት ሮጦ ሲሄድ ተመለከተ፡፡ ጨለማ ስለነበር ሊለየው አልቻለም::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመሴይ ማብዩፍ ኑሮ እያቆለቆለ ሄደ እንጂ አልተሻሻለም:: ባለፈው
ዓመት የሠራተኛቸውን ደመወዝ መክፈል አቅቶአቸው ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ የቤት ኪራይ መክፈል አቃታቸው፡፡ ቀስ በቀስ የቤቱን እቃ ሽጠው ጨረሱ፡፡ የጻፉትንም መጽሐፍ ገዢ ስላጣ እንደ አሮጌ መጽሐፍ ተቆጥሮ
በቅናሽ ሸጡት፡፡ ቀደም ሲል አልፎ አልፎ ሥጋ ይበሉ ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ጠፍቶ የሚበሉት ደረቅ ዳቦና የተቀቀለ ድንች ሆነ፡፡ በመጨረሻ
የሚሽጡት ንብረት ሁሉ አልቆ የቀረው በደህና ዘመን የሰበሰብዋቸውና በጣም የሚወዷቸው መጻሕፍት ብቻ ነበሩ፡፡ መሴይ ማብዩፍ የሚያነዱት እንጨት ስላልነበራቸው ገና ጀምበር ስትጠልቅ ይተኛሉ፡፡ ከጊዜ በኋላማ በጣም እየደኸዩ ስለሄዱ ጎረቤት ሀሉ ይሸሻቸው ጀመር:: ሰዎች እንደሚሸሹዋቸው ስለገባቸው እርሳቸውም ይሸሿቸዋል:: በልጅ ስቃይ
👍18👎1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ከየቤቱ መስኮት እየተንጠላጠለ ይሳሳቃሉ፣ ወጣቶች የነገሩን ምንነት ሳያጤኑ ጥልቅ ይላሉ፡፡ «ተነስ ተንቀሳቀስ» እያሉ ጩኸት ያስተጋባሉ፡ ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፓሪስ ከተማ ላይ የሆነውን ላውጋችሁ።
በየአውራ ጎዳናው፣ በየገበያ ቦታ፣ በየመንደሩ ትንፋሽ ያጠራቸው ሰዎች፣ሠራተኞችና ተማሪዎች፣ «ተነስ፣ ተንቀሳቀስ፣ ክንድህን አንሳ» እያለ በአንድ ቋንቋ ይጮሃሉ፡፡ የመንገድ መብራት፣ መስተዋት፣ የመጓጓዣ ጋሪዎችንና
ሠረገላዎችን ይበረብራሉ፣ ድንጋይ ይወረውራሉ፣ ቤት ውስጥ እየገቡ የቤት እቃ ያንኮታከታሉ፣ ሰሌዳ ይዘው በየመንገዱ ይዞራሉ፡፡ ማን
አስተባበራቸው? ማን አነሳሳቸው? ማን ያውቃል!
የአድመኞቹ ወላፈን እንደ ጭድ እሳት ተቀጣጠለ፡፡ በሦስት ሰዓት
ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ቁልፍ የሆኑትን ስፍራዎች ከቁጥጥራቸው ሥር አደረጉ፡፡ ከሰዓት በኋላ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ የፓሪስ ከተማን |
ሦስት አራተኛ የሚሆነውን ክፍል ያዘ:: ይህም ከድንጋይ ውርወራ ወደ ጦር መሣሪያ መጨበጥ አሸጋገራቸው:: አድመኞቹ የመሣሪያ መጋዘን ስለማረኩ የጦር መሣሪያ ከዚያ ዘረፉ:: በአሥራ ሁለት ሰዓት ቅልጥ ያለ ዝርፊያ
ተጀመረ።
በአንድ ፊት አድመኞቹ በሌላ አቅጣጫ የመንግሥት ወታደሮች
ሥፍራ ሥፍራቸውን ያዙ፡፡ ተኩሰ ተጧጧፈ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ያለ፣
ወደፊት በሚሆነው እጠቀማለሁ ብሎ ያለመ፤ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ
ጭምር ሁኔታውን ለማየት እየተሽሎከሎከ ወደ ጦር ሜዳው አመሩ፡፡እንደ እነቪክተር ህዩጎ ያለ አልጠግብ ባይ ከእሳተ ገሞራ ውስጥ ገብቶ መውጫ በማጣት ተቅበዘበዘ፡፡ ከጦርነቱ፡ መካከል በመግባታቸው ጥግ ይዘው
አውጣን» ከማለት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፡፡ ቅልጥ ያለ ጥይት እሩምታ ግማሽ ሰዓት ወሰደ:: የጦሩ ክፍል በያለበት መሯሯጥ፣መንቀሳቀስ ሆነ፡፡ ከጦር ሜዳው በብዛት የጦር ኃይል ጎረፈ:: ውጊያው ፓሪስ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡
የጦር ኃይሉ እንዳላ መንቀሳቀሱን የተመለከተ ሕዝብ ወደኋላ መሸሽ
ጀመረ፡፡ በየአቅጣጫው ተንሰራፍቶ የነበረው ሰልፈኛ እንደመበተን አለ::ትርምስምሱ ወጣ:: አንዳንዱማ ፈሪ በሩጫ እግሬ አውጪኝ አለ፡፡
ዝናብ በሀይል ይጥላል:: ከዚህ ትርምስ ውስጥ አንድ ልጅ ውራጅ
እቃ ከሚሽጥበት ሱቅ አካባቢ ብቅ አለ፡፡ አንዲት አሮጊት ሽጉጥ ይዘው መቀመጣቸውን ስለተመለከተ ልጁ ወደ ሴትዮዋ ሮጠ
«እማማ፣ አንድ ጊዜ ሽጉጥዎን ያውሱኛል?» ሲል ጠየቃቸው:::
ሽጉጡን ለማግኘት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ወዲያው መሣሪያውን ከእጁ አስገብቶ ወደ መጣበት ተመልሶ ሮጠ፡፡
ልጁ ከአሁን ቀደም ያነሳነው ሚስተር ቴናድዩ ከእስር ቤት እንዲያመልጥ የረዳውና ጋቭሮች የሚባለው ነበር፡፡ መንገድ ከጀመረ በኋላ ነበር ሽጉጡ
ጥይት እንደሌለው የተገነዘበው:: ቢሆንም መንገዱን ቀጠለ፡፡
እነ ኩርፌይራክና ኤንጆልሪስ ከቁጥጥራቸው ስር ካደረጉት ሰፈር ደረሰ:: ከሌላ አቅጣጫ ሌሎች በድኖች የሚመሩት የአድመኞች ቡድን መጥቶ ሲደባለቅ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮችም አብሮ ከሰልፈኞቹ ጋር ተደባለቀ::
««ወዴት ነው የምንሄደው?» ሲል ጠየቀ::
‹‹ተከተለን» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት::
የረብሻው ቀንደኛ መሪዎች ከአፍ እስከ ገደፍ ታጥቀዋል:: ከኋላ
የተከተላቸው ጀሌ አንዳንዱ የጦር መሣሪያ ሲይዝ አንዳንዱ ዱላ ብቻ ነው የያዘውን ፡፡ ከሠራዊቱ መካከል አንድ በእድሜ የገፉ ሽማግሌዎም ነበሩ::
ሽማግሌው ምንም ዓይነት የጦር መሣሪያ አልያዘም:: ግን በጣም እየተቻኮለ ነበር የሚሄዱት፡፡ ፊታቸውን ሲያዩት ከአሳብ ባህር የሰመጠ ይመስላል፡፡
ጋቭሮች ከሩቁ አያቸው::
«ያ ማነው?» ሲል ኩርፌይራክን ጠየቀው::
«አንድ ሽማግሌ ነዋ!» ሲል መለሰለት::
ከአሁን ቀደም ያየናቸው መሴይ ማብዩፍ ነበሩ::
ሽማግሌው ፊት ለፊት ከሚሄደው መስመር ሊደርሱ ምንም ያህል
አልቀራቸውም::
«ምን ዓይነት ቆራጥ ሽማግሌ ናቸው!» ሲሉ ተማሪዎቹ አጉረመረሙ። ማን እንደሆኑ ለማወቅ ተማሪዎቹ ጊዜ አልወሰደባቸውም ገዳም ውስጥ
ይኖሩ እንደነበር የሚያውቋቸው ሰዎች በሹክሹክታ ስማቸውን አስተጋቡ ሠራዊቱ አንዱን ጎዳና ጨርሶ ወደ ሌላው ተሸጋገረ፡፡ ጋቭሮችም መጓዙን ቀጠለ።
ብዙ በተጓዘ ቁጥር የሠራዊቱ ቁጥር እየጨመረ ሄደ፡፡ አንድ ግዙፍ ሰውነት ያለው ረጅም ሰው መጥቶ ተደባለቀ፡፡ ሽበት ጣል ጣል አድርጎበታል ፡መሪዎቹ ይህ ሰው ማን እንደሆነ አላወቁትም፡፡ ግን ወደ እነርሱ ለመጠጋት
በጣም ይፈልጋል፡፡ ጋቭሮች በሚያዜመው መዝሙር ተመስጦ ስለነበረ ሰውዬውን ልብ አላለውም፡፡ ልጁ መዝሙር ሲሰለቸው ያፏጫል፤ አንዳንዴ
ያንን ጥይት የሌለውን ሽጉጡን ያሻሻል፡፡
ሰልፈኛው መንገዱን ቀጥሎ እንደአጋጣሚ ሆኖ በኩርፌይራክ መኖሪያ ቤት ደጃፍ ያልፋል፡፡
«ጥሩ አጋጣሚ ነው» ይላል ኩርፌይራክ፡፡ «ቆቤ ጠፍቷል፤ ጠዋት ደግሞ ቦርሳዬን ረስቼ ነው የመጣሁት፡፡»
ከሰልፈኛው ተገንጥሎ ደረጃዎቹን በእጥፍ እየዘለለ ወደ ቤቱ ገባ
አንድ አሮጌ ቆብና የኪስ ቦርሳውን አነሳ፡፡ ከቆሻሻ ልብስ ውስጥ
የነበረ ሌላ አነስተኛ የእጅ ቦርሳም ወሰደ:: ደረጃውን በችኮላ ሲወርድ በጨለማ ውስጥ አንድ ሰው «ሊያነጋግርህ የሚፈልግ ሰው አለ» ሲል ነገረው፡፡
በዚህ ጊዜ አንድ የተቦጫጨቀ የሴት ቀሚስ ከላይ ያጠለቀ ወንድ
ከወደ ውስጥ ብቅ ብሎ አነጋገረው:: ድምፁ የሴት እንጂ የወንድ አይመስልም:: በጣም ቀጭን ነው::
«ማሪየስን አይተውታል?»
«የለም፤ ከቤት አልመጣም::»
«ማታ ይመጣ ይሆን?»
«እኔ እንጃ፡፡ እኔ ግን ዛሬ ወደቤት አልመለስም::»
አለባበሱና ድምፁ ሴት ያስመስለው ወጣት ኩርፌይራክን አፍጥጦ አየው
ለምን አይመለሱም?» ሲል በድፍረት ጠየቀው::
«ምክንያቱም...»
«እንግዲያው አንተ ወዴት ነው የምትሄደው?» በማለት ጣልቃ ገባ፡፡
«ምን ያደርግልሃል?»
«ቦርሳህን ልያዝልህ?»
«ወደ ጦርነቱ ቦታ ነው የምሄደው?»
«አብሬህ ብሄድ ትፈቅድልኛለህ?»
«ከፈለግህ፣ እኔ ምን ቸገረኝ» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት:: «መንገዱ
ነጻ፣ ጎዳናው የጋራ!»
ኩርፌይራክ ይህን እንደተናገረ ከጓደኞቹ ለመድረስ በሩጫ ወጣ፡፡
እንደደረሰም የእጅ ቦርሳውን እንዲይዝለት ለአንዱ ጓደኛው ሰጠው:: ከሩብ ሰዓት ጉዞ በኋላ መለስ ቢል ወጣቱ እንደተከተለው ተገነዘበ፡፡
ለአመዕ የተነሳሳ ሰልፈኛ ብዙውን ጊዜ የሚመራው በነፋስ ስለሆነ
አንዳንዴ ወደፈለገበት ሳይሆን ወደ አልፈለገበት አቅጣጫ ነው የሚጓዘው::ይህም በመሆኑ ይህ ሰልፈኛ ሴንትሜሪ ከተባለ ሥፍራ ለመሄድ ፈልጎ ሳይታወቀው ይህን ቦታ አልፎ ከሴንት ዴኒስ ይደርሳል፡፡
ከሰላሳ ዓመታት በፊት አንድ መንገደኛ ሴንት ዴኒስ ከተባለ ሥፍራ ቢያልፍ መንገዱ እየጠበበ ሄዶ በመጨረሻ እንደ አቁማዳ ጫፍ መደፈኑን ይገነዘብ ነበር፡፡ አካባቢውን አጥርቶ የማያውቅ ከሆነማ በግራና በቀኝ በኩል
የጨለማ መንገድ መኖሩን ስለማይረዳ መድረሻ ያጣል:: ውስጥ አዋቂ ግን በእነዚህ ጠባብ የጨለማ መንገዶች ተሹለክልኮ ሊያልፍ ይችላል፡፡ በስተቀኝ
በኩል ያለውን የቀኝ መንገድ ይዞ ሲጓዝ ከአንድ መሸታና ምግብ ቤት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ከየቤቱ መስኮት እየተንጠላጠለ ይሳሳቃሉ፣ ወጣቶች የነገሩን ምንነት ሳያጤኑ ጥልቅ ይላሉ፡፡ «ተነስ ተንቀሳቀስ» እያሉ ጩኸት ያስተጋባሉ፡ ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፓሪስ ከተማ ላይ የሆነውን ላውጋችሁ።
በየአውራ ጎዳናው፣ በየገበያ ቦታ፣ በየመንደሩ ትንፋሽ ያጠራቸው ሰዎች፣ሠራተኞችና ተማሪዎች፣ «ተነስ፣ ተንቀሳቀስ፣ ክንድህን አንሳ» እያለ በአንድ ቋንቋ ይጮሃሉ፡፡ የመንገድ መብራት፣ መስተዋት፣ የመጓጓዣ ጋሪዎችንና
ሠረገላዎችን ይበረብራሉ፣ ድንጋይ ይወረውራሉ፣ ቤት ውስጥ እየገቡ የቤት እቃ ያንኮታከታሉ፣ ሰሌዳ ይዘው በየመንገዱ ይዞራሉ፡፡ ማን
አስተባበራቸው? ማን አነሳሳቸው? ማን ያውቃል!
የአድመኞቹ ወላፈን እንደ ጭድ እሳት ተቀጣጠለ፡፡ በሦስት ሰዓት
ጊዜ ውስጥ አንዳንድ ቁልፍ የሆኑትን ስፍራዎች ከቁጥጥራቸው ሥር አደረጉ፡፡ ከሰዓት በኋላ ወደ አሥራ አንድ ሰዓት ገደማ የፓሪስ ከተማን |
ሦስት አራተኛ የሚሆነውን ክፍል ያዘ:: ይህም ከድንጋይ ውርወራ ወደ ጦር መሣሪያ መጨበጥ አሸጋገራቸው:: አድመኞቹ የመሣሪያ መጋዘን ስለማረኩ የጦር መሣሪያ ከዚያ ዘረፉ:: በአሥራ ሁለት ሰዓት ቅልጥ ያለ ዝርፊያ
ተጀመረ።
በአንድ ፊት አድመኞቹ በሌላ አቅጣጫ የመንግሥት ወታደሮች
ሥፍራ ሥፍራቸውን ያዙ፡፡ ተኩሰ ተጧጧፈ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ያለ፣
ወደፊት በሚሆነው እጠቀማለሁ ብሎ ያለመ፤ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ
ጭምር ሁኔታውን ለማየት እየተሽሎከሎከ ወደ ጦር ሜዳው አመሩ፡፡እንደ እነቪክተር ህዩጎ ያለ አልጠግብ ባይ ከእሳተ ገሞራ ውስጥ ገብቶ መውጫ በማጣት ተቅበዘበዘ፡፡ ከጦርነቱ፡ መካከል በመግባታቸው ጥግ ይዘው
አውጣን» ከማለት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፡፡ ቅልጥ ያለ ጥይት እሩምታ ግማሽ ሰዓት ወሰደ:: የጦሩ ክፍል በያለበት መሯሯጥ፣መንቀሳቀስ ሆነ፡፡ ከጦር ሜዳው በብዛት የጦር ኃይል ጎረፈ:: ውጊያው ፓሪስ ከተማ ውስጥ ነበር፡፡
የጦር ኃይሉ እንዳላ መንቀሳቀሱን የተመለከተ ሕዝብ ወደኋላ መሸሽ
ጀመረ፡፡ በየአቅጣጫው ተንሰራፍቶ የነበረው ሰልፈኛ እንደመበተን አለ::ትርምስምሱ ወጣ:: አንዳንዱማ ፈሪ በሩጫ እግሬ አውጪኝ አለ፡፡
ዝናብ በሀይል ይጥላል:: ከዚህ ትርምስ ውስጥ አንድ ልጅ ውራጅ
እቃ ከሚሽጥበት ሱቅ አካባቢ ብቅ አለ፡፡ አንዲት አሮጊት ሽጉጥ ይዘው መቀመጣቸውን ስለተመለከተ ልጁ ወደ ሴትዮዋ ሮጠ
«እማማ፣ አንድ ጊዜ ሽጉጥዎን ያውሱኛል?» ሲል ጠየቃቸው:::
ሽጉጡን ለማግኘት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ወዲያው መሣሪያውን ከእጁ አስገብቶ ወደ መጣበት ተመልሶ ሮጠ፡፡
ልጁ ከአሁን ቀደም ያነሳነው ሚስተር ቴናድዩ ከእስር ቤት እንዲያመልጥ የረዳውና ጋቭሮች የሚባለው ነበር፡፡ መንገድ ከጀመረ በኋላ ነበር ሽጉጡ
ጥይት እንደሌለው የተገነዘበው:: ቢሆንም መንገዱን ቀጠለ፡፡
እነ ኩርፌይራክና ኤንጆልሪስ ከቁጥጥራቸው ስር ካደረጉት ሰፈር ደረሰ:: ከሌላ አቅጣጫ ሌሎች በድኖች የሚመሩት የአድመኞች ቡድን መጥቶ ሲደባለቅ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮችም አብሮ ከሰልፈኞቹ ጋር ተደባለቀ::
««ወዴት ነው የምንሄደው?» ሲል ጠየቀ::
‹‹ተከተለን» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት::
የረብሻው ቀንደኛ መሪዎች ከአፍ እስከ ገደፍ ታጥቀዋል:: ከኋላ
የተከተላቸው ጀሌ አንዳንዱ የጦር መሣሪያ ሲይዝ አንዳንዱ ዱላ ብቻ ነው የያዘውን ፡፡ ከሠራዊቱ መካከል አንድ በእድሜ የገፉ ሽማግሌዎም ነበሩ::
ሽማግሌው ምንም ዓይነት የጦር መሣሪያ አልያዘም:: ግን በጣም እየተቻኮለ ነበር የሚሄዱት፡፡ ፊታቸውን ሲያዩት ከአሳብ ባህር የሰመጠ ይመስላል፡፡
ጋቭሮች ከሩቁ አያቸው::
«ያ ማነው?» ሲል ኩርፌይራክን ጠየቀው::
«አንድ ሽማግሌ ነዋ!» ሲል መለሰለት::
ከአሁን ቀደም ያየናቸው መሴይ ማብዩፍ ነበሩ::
ሽማግሌው ፊት ለፊት ከሚሄደው መስመር ሊደርሱ ምንም ያህል
አልቀራቸውም::
«ምን ዓይነት ቆራጥ ሽማግሌ ናቸው!» ሲሉ ተማሪዎቹ አጉረመረሙ። ማን እንደሆኑ ለማወቅ ተማሪዎቹ ጊዜ አልወሰደባቸውም ገዳም ውስጥ
ይኖሩ እንደነበር የሚያውቋቸው ሰዎች በሹክሹክታ ስማቸውን አስተጋቡ ሠራዊቱ አንዱን ጎዳና ጨርሶ ወደ ሌላው ተሸጋገረ፡፡ ጋቭሮችም መጓዙን ቀጠለ።
ብዙ በተጓዘ ቁጥር የሠራዊቱ ቁጥር እየጨመረ ሄደ፡፡ አንድ ግዙፍ ሰውነት ያለው ረጅም ሰው መጥቶ ተደባለቀ፡፡ ሽበት ጣል ጣል አድርጎበታል ፡መሪዎቹ ይህ ሰው ማን እንደሆነ አላወቁትም፡፡ ግን ወደ እነርሱ ለመጠጋት
በጣም ይፈልጋል፡፡ ጋቭሮች በሚያዜመው መዝሙር ተመስጦ ስለነበረ ሰውዬውን ልብ አላለውም፡፡ ልጁ መዝሙር ሲሰለቸው ያፏጫል፤ አንዳንዴ
ያንን ጥይት የሌለውን ሽጉጡን ያሻሻል፡፡
ሰልፈኛው መንገዱን ቀጥሎ እንደአጋጣሚ ሆኖ በኩርፌይራክ መኖሪያ ቤት ደጃፍ ያልፋል፡፡
«ጥሩ አጋጣሚ ነው» ይላል ኩርፌይራክ፡፡ «ቆቤ ጠፍቷል፤ ጠዋት ደግሞ ቦርሳዬን ረስቼ ነው የመጣሁት፡፡»
ከሰልፈኛው ተገንጥሎ ደረጃዎቹን በእጥፍ እየዘለለ ወደ ቤቱ ገባ
አንድ አሮጌ ቆብና የኪስ ቦርሳውን አነሳ፡፡ ከቆሻሻ ልብስ ውስጥ
የነበረ ሌላ አነስተኛ የእጅ ቦርሳም ወሰደ:: ደረጃውን በችኮላ ሲወርድ በጨለማ ውስጥ አንድ ሰው «ሊያነጋግርህ የሚፈልግ ሰው አለ» ሲል ነገረው፡፡
በዚህ ጊዜ አንድ የተቦጫጨቀ የሴት ቀሚስ ከላይ ያጠለቀ ወንድ
ከወደ ውስጥ ብቅ ብሎ አነጋገረው:: ድምፁ የሴት እንጂ የወንድ አይመስልም:: በጣም ቀጭን ነው::
«ማሪየስን አይተውታል?»
«የለም፤ ከቤት አልመጣም::»
«ማታ ይመጣ ይሆን?»
«እኔ እንጃ፡፡ እኔ ግን ዛሬ ወደቤት አልመለስም::»
አለባበሱና ድምፁ ሴት ያስመስለው ወጣት ኩርፌይራክን አፍጥጦ አየው
ለምን አይመለሱም?» ሲል በድፍረት ጠየቀው::
«ምክንያቱም...»
«እንግዲያው አንተ ወዴት ነው የምትሄደው?» በማለት ጣልቃ ገባ፡፡
«ምን ያደርግልሃል?»
«ቦርሳህን ልያዝልህ?»
«ወደ ጦርነቱ ቦታ ነው የምሄደው?»
«አብሬህ ብሄድ ትፈቅድልኛለህ?»
«ከፈለግህ፣ እኔ ምን ቸገረኝ» ሲል ኩርፌይራክ መለሰለት:: «መንገዱ
ነጻ፣ ጎዳናው የጋራ!»
ኩርፌይራክ ይህን እንደተናገረ ከጓደኞቹ ለመድረስ በሩጫ ወጣ፡፡
እንደደረሰም የእጅ ቦርሳውን እንዲይዝለት ለአንዱ ጓደኛው ሰጠው:: ከሩብ ሰዓት ጉዞ በኋላ መለስ ቢል ወጣቱ እንደተከተለው ተገነዘበ፡፡
ለአመዕ የተነሳሳ ሰልፈኛ ብዙውን ጊዜ የሚመራው በነፋስ ስለሆነ
አንዳንዴ ወደፈለገበት ሳይሆን ወደ አልፈለገበት አቅጣጫ ነው የሚጓዘው::ይህም በመሆኑ ይህ ሰልፈኛ ሴንትሜሪ ከተባለ ሥፍራ ለመሄድ ፈልጎ ሳይታወቀው ይህን ቦታ አልፎ ከሴንት ዴኒስ ይደርሳል፡፡
ከሰላሳ ዓመታት በፊት አንድ መንገደኛ ሴንት ዴኒስ ከተባለ ሥፍራ ቢያልፍ መንገዱ እየጠበበ ሄዶ በመጨረሻ እንደ አቁማዳ ጫፍ መደፈኑን ይገነዘብ ነበር፡፡ አካባቢውን አጥርቶ የማያውቅ ከሆነማ በግራና በቀኝ በኩል
የጨለማ መንገድ መኖሩን ስለማይረዳ መድረሻ ያጣል:: ውስጥ አዋቂ ግን በእነዚህ ጠባብ የጨለማ መንገዶች ተሹለክልኮ ሊያልፍ ይችላል፡፡ በስተቀኝ
በኩል ያለውን የቀኝ መንገድ ይዞ ሲጓዝ ከአንድ መሸታና ምግብ ቤት
👍14😁2
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...እውነትም ቦታው እስትራቴጂካዊ ነበር በአንድ በኩል ወደቤቱ ሚያስገባው መንገድ ሰፊ ነው:: በጓሮ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ቀጭን የጨለማ መንገድ አለው:: ማንኛውም አጥቂ ጦር በሴንት ዴኒስ
ጎዳና በኩል ባለው ሰፊ ጎዳና እንጂ በጓሮ በኩል ደፍሮ ሊገባ አይችልም::ስለዚህ የፊት ለፊቱን አጥብቀው ከያዙ የኋላውን በቀላሉ መመከት ይቻላል።
ድንገት ማፈግፈግም ቢመጣ በጓሮ በኩል የማምለጥ እድል አለ::
ያ ሁሉ ሕዝብ ሆ እያለ መለስ ሲል መንገዱ ሁሉ ጨነቀው::
ባለሱቅ ቶሎ ብሎ ሱቁን ዘጋ:: ከግራና ከቀኝ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የውጭ በር ካላቸው የውጭ በራቸውን፣ አለዚያም የየቤታቸውን በርና መስኮት ቀረቀሩ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ባይ መስኮቱን ከፍቶ በትንሹ ያያል፡፡ አላስችል
ያለውና «ምን ይቀርብኛል ብሎ ተስፋ የቆረጠው ከሰልፈኛው ጋር
ይደባለቃል፡፡
አንዲት በጣም የተደናገጠች አርጊት ምን አደረገች? ቶሎ ብላ አሮጌ ፍራሽ ከውጭ በኩል በገመድ በማንጠልጠል መስኮትዋን ሸፈነችው:: ሌላ
ፍራሽ ደግሞ ከውስጥ በኩል በማቆም ጋረደችው፡፡ ከዚያም ከመስኮቱ በር ወለል ላይ ለጥ ብላ ተኛች:: ጥይት ሲተኮስ እንዳይመታት ነበር፡፡
በዚያ አካባቢ በርና መስኮቱ የተከፈተ ቤት ሲኖር ያ መሸታ ቤትና ምግብ ቤት ብቻ ነበር:: ይሄ ደግሞ ያለ ምክንያት አልነበረም:: ትርምሱ፣ ጩኸቱ፣ ስድቡና
መዝሙሩ ድብልቅል ያለ ስለነበር የምጽዓት ቀን የመጣ
ስላስመሰለው ነው::
“ወያኔ ፣ ወይኔ፣ አምላኬ የዛሬን! ከዛሬው ብቻ ሰውረኝ» አሉ ማዳም ኻሽሉፕ ፡
ወዲያው በሃያ ደቂቃ ውስጥ ከሴትዮዋ መጠጥና ምግብ ቤት ምሽግ ተሠራ፡፡ በርሜሎች ተለቃቅመው በአሸዋና ጠጠር ተሞሉ፡፡ ጋብሮች በርሜል በማንከባለል ረዳ፡፡ በርሜል ሊሸፍነው ያልቻለውን ቦታ በአፈርና
በድንጋይ ቁልል ታጠረ፡፡ ኤንጂልራስ በጓሮው በኩል ወዳለው ጨለማ መንገድ የሚወስደውን በር ወለል አድርጎ ከፈተው:: ከዚያም ከቤቱ በር
ወደሚገኘው እቃ ማስቀመጫ ክፍል ወረደ:: ከምድር ቤቱ ውስጥ ወደሚገኘው ጥቂት በርሜሎችን አገኘ፡፡ እነርሱንም ለምሽግ ሥራ ተጠቀሙባቸው::መቼም እጅ ከተባበረ የማይሠራው ሥራ የለምና «ብዙ ቀናት ፈጅቷል
ተብሎ ሊገመት የሚችል ምሽግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡ በዚያች አጭር ሰዓት ያ ቤት ከቡናና ምግብ ቤትነት ወደ ጦር ካምፕ ተሸጋገረ::
አንድ ጋሪ ሴቶችን ጭኖ በዚያ በኩል ለማለፍ ይመጣል፡፡ ከሰልፈኞቹ መሪ አንደኛው ሮጦ ሄዶ ባለጋሪውንና ሴቶችን ካስወረደ በኋላ ሴቶቹን
ከይቅርታ ጋር አሰናበታቸው:: የፈረሱን ልጓም ይዞ በመጐተት ጋሪውን ወደ ምሽጉ ወሰደው::
«ጋሪ ደግሞ በዚህ ሰዓት፣ በዚህ መንገድ ምን ያደርጋል?» ሲል
ጠየቀ፡፡ «ከአሁን ቀደም በዚህ መንገድ ጋሪ አልፎ አያውቅም» ብሎ ከተናገረ በኋላ ፈረሱን ከጋሪው አላቅቆ አባረረው:: ፈረሱ ከሄደ በኋላ ጋሪውን በጎን
በማጋደም ያንን መንገድ ለመዝጋት ተጠቀመበት::
ማዳም ኸሽሉፕ ተናደዱ፣ የሚያደርጉትን ስላጡ ከአንደኛው ፎቅ ቁጭ ብለው ቀሩ፡፡ ዓይናቸው ከወዲያ ወዲህ ይቅበዘበዛል፡፡ፀ ሳይታወቃቸው እንባቸው በጉንጫቸው እንደ ጎርፍ ይወርዳል፡፡ ድምፅ አሰምተው ለማልቀስ ተሰብረዋል
አልደፈሩም::
«ምፅዓት ነው ይሄ» ሲሉ አጉረመረሙ::
ከሰካራሙ አንደኛው መጥቶ ጉንጫቸውን ከሳመ በኋላ «መቼም
እንደ ሴት ጉንጭ የሚለሰልስ ነገር የለም» ይላል፡፡
ቫውደር የተባለች ሠራተኛ እነርሱ ከነበሩበት ክፍል ገባች:: ከሰካራሞች ሌላው በሳቅ እየተፍነከነከ የሴትዮዋን ጨርቅ በመጎተት ወደ መስኮት
ወሰዳቸው:: ወደ ጆሮአቸው ተጠግቶ አናገራቸው::
«ቫውደር እኮ በጣም ፉንጋ ናት:: መቼስ ለፉንጋዎች ምሳሌ ሆና |
ልትቀርብ የምትችል ናት:: »
ወዲያው ኤንጆልራስ ጮክ እያለ ተናገረ፡፡
«እናንተ ሰካራሞች የምሽጉን ስም አታጉድፉ:: ቶሎ እንዲበርድላቸው
ከዚህ ሂዱና ከምትተኙበት ተኙ፡፡ ይህ ሥፍራ በአገር ፍቅር ለነደዱ እንጂ ለሰካራሞቹ አይደለም
ከሰካራሞቹ ማለትም ብዙም ያልጠነበዘው በዚህ ስድብ
ከተሞላበት ንግግር ስሜቱ በጣም ስለተነካ ውሃ በጣሳ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለበሰ፡፡ የውሃው ቅዝቃዜ እውነትም ስካሩን ትንሽ አበረደለት:: ወደ መስኮቱ ሄዶ ኢንጆልራስን ጥያቄ ጠየቀው::
«ከዚሁ ልተኛ?»
የለም፣ ከምትተኛበት ሂድና ተኛ እንጂ ከዚህ መተኛት አይቻልም::»
«እባካችሁ ነፍሴ እስክትወጣ ከዚሁ ልተኛ» ሲል ሰካራሙ በለዘበ አነጋገር ተናገረ፡፡
ኢንጆልራስ በንቀት ዓይን አየው:: ሰካራሙም የሚባለውን ሳይሰማ
ጥቂት ከተንተባተበ በኋላ አጠገቡ ከነበረው ጠረጴዛ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ብዙም ሳይቆይ እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ቸ
ዝናቡ ቆሞአል፡፡ ተጨማሪ ሰልፈኛ የተለያየ መሳርሪያ እየያዘ መጣ፡፡
በሩቁ የምትታይ አንዲት የመንገድ መብራት ብቻ ነበረች:: እስዋም ብዙ አልቆየችም፤ ሰልፈኞቹ ሰበርዋት:: የተቀሩት መብራቶች ቀደም ሲል
ተሰብረዋል፡፡
ኢንጆልራስ፣ ካምብፌራና ከርፌይራክ ለሰልፈኛው አመራር መስጠት ጀመሩ፡፡ መንገዱ በሁለቱም አቅጣጫ በምሽግ ተዘጋ:: የጦር መሣሪያ የያዙ
ሁሉ ቦታ ቦታቸውን ያዙ:: አንዳንዶቹ ቆብ መሳይ ነገር አጥልቀዋል::አንዳንዱ በአጭር ታጥቆ ጎራዴ ሲይዝ ሌላው ጠብመንጃ አንግቷል።
መሣሪያ ይዞ ፈረስ ላይ የተቀመጠም አለ፡፡ አንዳንዱ የመጨረሻው ሰው እስከቀረ ድረስ እንዋጋለን» እያለ ይፎክራል፡፡ ሌላው ጥይት ሲያልቅ
በድንጋይ እንማታለን» ይላል:: አንዱ ያቅራራል፣ ሌላው ይሸልላል::አንዳንዱም እነርሱ ሲጠቁ የከተማው ሰው እንደሚደርስላቻው እርስ በእርስ
ይወያያል፡፡ ሁሉም በየፊናው ይነጋገራል፤ ይቻኮላል፤ ሥራ ለመሥራትና ቦታ ለመያዝ ይጣደፋል፡፡ ሰካራሞቹና የቡና ቤቱ ባለቤት የሚያደርጉትን
አጥተው ከአንድ ክፍል ውስጥ ተፋጥጠው ቁጭ ብለዋል::
ከቁመቱ፡ ዘለግ ያለውና የሰልፈኛው መሪ የሆነው ሰው ከሰልፈኛው መካከል ገብቶ ምሽግ ይሠራል:: ጋብሮችም ከምሽጉ ጫፍ ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል:: ማሪየስን የጠየቀውና ኩርፊያሪክን ጠብቀኝ
ያለው የሴት መልክ ያለው ግለሰብ ግን ከዚያ አልነበረም፡፡ ጋብሮትች
ከደስታው ብዛት ከወዲህ ወዲያ የሚለው እየዘፈነ ስለነበር አብዛኛው ሰልፈኛ ለይቶታል:: እንዲያውም ከነአካቴው ሰው ሁሉ የእርሱን ንቃትና ሞራል እያየ በጣም ተደፋፈረ፣ ሰነፉንና ዳተኛውን አነቃቃ:: ለፈሪውም
ልብ ዋጀለት። ለተደነባበረውም መንገድ ከፈተለት።
ጋብሮች ከአሮጊትዋ በነጠቀው ሽጉጥ ስላልረካ «ጠብመንጃ
እፈልጋለሁ፣ ምነው ብትሰጡኝ» እያለ ይጠይቃል::
«ጠብመንጃ ለአንተ ነው ወይስ ለማነው?» ሲል ካምብፌሪ ጠየቀው
«ምነው?» ሲል ጋብሮች ጥያቄን በጥያቄ ይመልሳል፡፡ «ምን ይጉድለኛል? ድሮ እኮ እንዴት ያለ ጠብመንጃ ነበረኝ» ሲል ይሸልላል::
ኢንጆልራስ ይስቃል፡፡
«አዋቂዎቹ ሲዳረሳቸው ለልጆች ይሰጣል::»
ጋብሮች በቁጣ ዞር ብሎ ይመልሳል፡፡
«አንተን ከእኔ በፊት ከገደሉህ እኔ እኮ ነኝ አንተን የምተካው:: ላከወ
«ጉረኛ» ሲል በቀልድ መልክ ኢንጆልሪስ መለሰለት::
«ጉረኛ አልከኝ?» ሲል ጋቭሮች ቃሉን ደገመ:: ይህን እንደጠየቀ
አንድ ሰው ከሰልፉ ወጥቶ ያያል:: ሮጦ ሄዶ «ከሰልፈኛው ተለይተው
አይሄዱ፤ ለዚህች ምስኪን አገር የሚውሉት ውለታ ቢኖር አሁን ነው፤ ስለዚህ አይሂዱ» ሲል ይማጠናቸዋል፡፡ ሰውየው ግን ፈጠን ብለው በመራመድ
ይሄዳሉ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...እውነትም ቦታው እስትራቴጂካዊ ነበር በአንድ በኩል ወደቤቱ ሚያስገባው መንገድ ሰፊ ነው:: በጓሮ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ቀጭን የጨለማ መንገድ አለው:: ማንኛውም አጥቂ ጦር በሴንት ዴኒስ
ጎዳና በኩል ባለው ሰፊ ጎዳና እንጂ በጓሮ በኩል ደፍሮ ሊገባ አይችልም::ስለዚህ የፊት ለፊቱን አጥብቀው ከያዙ የኋላውን በቀላሉ መመከት ይቻላል።
ድንገት ማፈግፈግም ቢመጣ በጓሮ በኩል የማምለጥ እድል አለ::
ያ ሁሉ ሕዝብ ሆ እያለ መለስ ሲል መንገዱ ሁሉ ጨነቀው::
ባለሱቅ ቶሎ ብሎ ሱቁን ዘጋ:: ከግራና ከቀኝ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የውጭ በር ካላቸው የውጭ በራቸውን፣ አለዚያም የየቤታቸውን በርና መስኮት ቀረቀሩ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ባይ መስኮቱን ከፍቶ በትንሹ ያያል፡፡ አላስችል
ያለውና «ምን ይቀርብኛል ብሎ ተስፋ የቆረጠው ከሰልፈኛው ጋር
ይደባለቃል፡፡
አንዲት በጣም የተደናገጠች አርጊት ምን አደረገች? ቶሎ ብላ አሮጌ ፍራሽ ከውጭ በኩል በገመድ በማንጠልጠል መስኮትዋን ሸፈነችው:: ሌላ
ፍራሽ ደግሞ ከውስጥ በኩል በማቆም ጋረደችው፡፡ ከዚያም ከመስኮቱ በር ወለል ላይ ለጥ ብላ ተኛች:: ጥይት ሲተኮስ እንዳይመታት ነበር፡፡
በዚያ አካባቢ በርና መስኮቱ የተከፈተ ቤት ሲኖር ያ መሸታ ቤትና ምግብ ቤት ብቻ ነበር:: ይሄ ደግሞ ያለ ምክንያት አልነበረም:: ትርምሱ፣ ጩኸቱ፣ ስድቡና
መዝሙሩ ድብልቅል ያለ ስለነበር የምጽዓት ቀን የመጣ
ስላስመሰለው ነው::
“ወያኔ ፣ ወይኔ፣ አምላኬ የዛሬን! ከዛሬው ብቻ ሰውረኝ» አሉ ማዳም ኻሽሉፕ ፡
ወዲያው በሃያ ደቂቃ ውስጥ ከሴትዮዋ መጠጥና ምግብ ቤት ምሽግ ተሠራ፡፡ በርሜሎች ተለቃቅመው በአሸዋና ጠጠር ተሞሉ፡፡ ጋብሮች በርሜል በማንከባለል ረዳ፡፡ በርሜል ሊሸፍነው ያልቻለውን ቦታ በአፈርና
በድንጋይ ቁልል ታጠረ፡፡ ኤንጂልራስ በጓሮው በኩል ወዳለው ጨለማ መንገድ የሚወስደውን በር ወለል አድርጎ ከፈተው:: ከዚያም ከቤቱ በር
ወደሚገኘው እቃ ማስቀመጫ ክፍል ወረደ:: ከምድር ቤቱ ውስጥ ወደሚገኘው ጥቂት በርሜሎችን አገኘ፡፡ እነርሱንም ለምሽግ ሥራ ተጠቀሙባቸው::መቼም እጅ ከተባበረ የማይሠራው ሥራ የለምና «ብዙ ቀናት ፈጅቷል
ተብሎ ሊገመት የሚችል ምሽግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡ በዚያች አጭር ሰዓት ያ ቤት ከቡናና ምግብ ቤትነት ወደ ጦር ካምፕ ተሸጋገረ::
አንድ ጋሪ ሴቶችን ጭኖ በዚያ በኩል ለማለፍ ይመጣል፡፡ ከሰልፈኞቹ መሪ አንደኛው ሮጦ ሄዶ ባለጋሪውንና ሴቶችን ካስወረደ በኋላ ሴቶቹን
ከይቅርታ ጋር አሰናበታቸው:: የፈረሱን ልጓም ይዞ በመጐተት ጋሪውን ወደ ምሽጉ ወሰደው::
«ጋሪ ደግሞ በዚህ ሰዓት፣ በዚህ መንገድ ምን ያደርጋል?» ሲል
ጠየቀ፡፡ «ከአሁን ቀደም በዚህ መንገድ ጋሪ አልፎ አያውቅም» ብሎ ከተናገረ በኋላ ፈረሱን ከጋሪው አላቅቆ አባረረው:: ፈረሱ ከሄደ በኋላ ጋሪውን በጎን
በማጋደም ያንን መንገድ ለመዝጋት ተጠቀመበት::
ማዳም ኸሽሉፕ ተናደዱ፣ የሚያደርጉትን ስላጡ ከአንደኛው ፎቅ ቁጭ ብለው ቀሩ፡፡ ዓይናቸው ከወዲያ ወዲህ ይቅበዘበዛል፡፡ፀ ሳይታወቃቸው እንባቸው በጉንጫቸው እንደ ጎርፍ ይወርዳል፡፡ ድምፅ አሰምተው ለማልቀስ ተሰብረዋል
አልደፈሩም::
«ምፅዓት ነው ይሄ» ሲሉ አጉረመረሙ::
ከሰካራሙ አንደኛው መጥቶ ጉንጫቸውን ከሳመ በኋላ «መቼም
እንደ ሴት ጉንጭ የሚለሰልስ ነገር የለም» ይላል፡፡
ቫውደር የተባለች ሠራተኛ እነርሱ ከነበሩበት ክፍል ገባች:: ከሰካራሞች ሌላው በሳቅ እየተፍነከነከ የሴትዮዋን ጨርቅ በመጎተት ወደ መስኮት
ወሰዳቸው:: ወደ ጆሮአቸው ተጠግቶ አናገራቸው::
«ቫውደር እኮ በጣም ፉንጋ ናት:: መቼስ ለፉንጋዎች ምሳሌ ሆና |
ልትቀርብ የምትችል ናት:: »
ወዲያው ኤንጆልራስ ጮክ እያለ ተናገረ፡፡
«እናንተ ሰካራሞች የምሽጉን ስም አታጉድፉ:: ቶሎ እንዲበርድላቸው
ከዚህ ሂዱና ከምትተኙበት ተኙ፡፡ ይህ ሥፍራ በአገር ፍቅር ለነደዱ እንጂ ለሰካራሞቹ አይደለም
ከሰካራሞቹ ማለትም ብዙም ያልጠነበዘው በዚህ ስድብ
ከተሞላበት ንግግር ስሜቱ በጣም ስለተነካ ውሃ በጣሳ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለበሰ፡፡ የውሃው ቅዝቃዜ እውነትም ስካሩን ትንሽ አበረደለት:: ወደ መስኮቱ ሄዶ ኢንጆልራስን ጥያቄ ጠየቀው::
«ከዚሁ ልተኛ?»
የለም፣ ከምትተኛበት ሂድና ተኛ እንጂ ከዚህ መተኛት አይቻልም::»
«እባካችሁ ነፍሴ እስክትወጣ ከዚሁ ልተኛ» ሲል ሰካራሙ በለዘበ አነጋገር ተናገረ፡፡
ኢንጆልራስ በንቀት ዓይን አየው:: ሰካራሙም የሚባለውን ሳይሰማ
ጥቂት ከተንተባተበ በኋላ አጠገቡ ከነበረው ጠረጴዛ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ብዙም ሳይቆይ እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ቸ
ዝናቡ ቆሞአል፡፡ ተጨማሪ ሰልፈኛ የተለያየ መሳርሪያ እየያዘ መጣ፡፡
በሩቁ የምትታይ አንዲት የመንገድ መብራት ብቻ ነበረች:: እስዋም ብዙ አልቆየችም፤ ሰልፈኞቹ ሰበርዋት:: የተቀሩት መብራቶች ቀደም ሲል
ተሰብረዋል፡፡
ኢንጆልራስ፣ ካምብፌራና ከርፌይራክ ለሰልፈኛው አመራር መስጠት ጀመሩ፡፡ መንገዱ በሁለቱም አቅጣጫ በምሽግ ተዘጋ:: የጦር መሣሪያ የያዙ
ሁሉ ቦታ ቦታቸውን ያዙ:: አንዳንዶቹ ቆብ መሳይ ነገር አጥልቀዋል::አንዳንዱ በአጭር ታጥቆ ጎራዴ ሲይዝ ሌላው ጠብመንጃ አንግቷል።
መሣሪያ ይዞ ፈረስ ላይ የተቀመጠም አለ፡፡ አንዳንዱ የመጨረሻው ሰው እስከቀረ ድረስ እንዋጋለን» እያለ ይፎክራል፡፡ ሌላው ጥይት ሲያልቅ
በድንጋይ እንማታለን» ይላል:: አንዱ ያቅራራል፣ ሌላው ይሸልላል::አንዳንዱም እነርሱ ሲጠቁ የከተማው ሰው እንደሚደርስላቻው እርስ በእርስ
ይወያያል፡፡ ሁሉም በየፊናው ይነጋገራል፤ ይቻኮላል፤ ሥራ ለመሥራትና ቦታ ለመያዝ ይጣደፋል፡፡ ሰካራሞቹና የቡና ቤቱ ባለቤት የሚያደርጉትን
አጥተው ከአንድ ክፍል ውስጥ ተፋጥጠው ቁጭ ብለዋል::
ከቁመቱ፡ ዘለግ ያለውና የሰልፈኛው መሪ የሆነው ሰው ከሰልፈኛው መካከል ገብቶ ምሽግ ይሠራል:: ጋብሮችም ከምሽጉ ጫፍ ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል:: ማሪየስን የጠየቀውና ኩርፊያሪክን ጠብቀኝ
ያለው የሴት መልክ ያለው ግለሰብ ግን ከዚያ አልነበረም፡፡ ጋብሮትች
ከደስታው ብዛት ከወዲህ ወዲያ የሚለው እየዘፈነ ስለነበር አብዛኛው ሰልፈኛ ለይቶታል:: እንዲያውም ከነአካቴው ሰው ሁሉ የእርሱን ንቃትና ሞራል እያየ በጣም ተደፋፈረ፣ ሰነፉንና ዳተኛውን አነቃቃ:: ለፈሪውም
ልብ ዋጀለት። ለተደነባበረውም መንገድ ከፈተለት።
ጋብሮች ከአሮጊትዋ በነጠቀው ሽጉጥ ስላልረካ «ጠብመንጃ
እፈልጋለሁ፣ ምነው ብትሰጡኝ» እያለ ይጠይቃል::
«ጠብመንጃ ለአንተ ነው ወይስ ለማነው?» ሲል ካምብፌሪ ጠየቀው
«ምነው?» ሲል ጋብሮች ጥያቄን በጥያቄ ይመልሳል፡፡ «ምን ይጉድለኛል? ድሮ እኮ እንዴት ያለ ጠብመንጃ ነበረኝ» ሲል ይሸልላል::
ኢንጆልራስ ይስቃል፡፡
«አዋቂዎቹ ሲዳረሳቸው ለልጆች ይሰጣል::»
ጋብሮች በቁጣ ዞር ብሎ ይመልሳል፡፡
«አንተን ከእኔ በፊት ከገደሉህ እኔ እኮ ነኝ አንተን የምተካው:: ላከወ
«ጉረኛ» ሲል በቀልድ መልክ ኢንጆልሪስ መለሰለት::
«ጉረኛ አልከኝ?» ሲል ጋቭሮች ቃሉን ደገመ:: ይህን እንደጠየቀ
አንድ ሰው ከሰልፉ ወጥቶ ያያል:: ሮጦ ሄዶ «ከሰልፈኛው ተለይተው
አይሄዱ፤ ለዚህች ምስኪን አገር የሚውሉት ውለታ ቢኖር አሁን ነው፤ ስለዚህ አይሂዱ» ሲል ይማጠናቸዋል፡፡ ሰውየው ግን ፈጠን ብለው በመራመድ
ይሄዳሉ፡፡
👍12
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡
ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)
ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡
ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::
«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»
« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»
«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»
«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡
«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።
በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::
“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»
«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::
«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::
«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»
«አልችልም ጌታው::»
ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::
«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው
«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::
ሸ
«እምቢ አልክ?»
«አዎን የእኔ ጀግ…»
የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::
«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::
«እጅ ወደ ላይ!» አለው::
ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡
«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡
የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።
ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡
«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»
ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::
ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡
«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»
ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::
ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡
«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::
የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡
«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::
«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡
ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)
ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡
ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡
ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::
«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»
« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»
«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»
«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡
«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።
በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::
“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»
«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::
«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::
«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»
«አልችልም ጌታው::»
ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::
«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው
«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::
ሸ
«እምቢ አልክ?»
«አዎን የእኔ ጀግ…»
የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::
«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::
«እጅ ወደ ላይ!» አለው::
ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡
«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡
የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።
ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡
«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»
ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::
ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡
«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»
ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::
ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡
«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::
የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡
«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::
«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡
ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
👍9
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ኢንጆልራስ ጎንበስ ብሎ የራሣውን ጭንቅላት ቀና ካደረገ በኋላ ግምባሩን ሳመው፡፡
መሞቱን በመርሳት በጥንቃቄ ያልያዘው እንደሆነ የሚያምመው ይመስል ቀስ ብሎ በክርኑ ደግፎ ቀና አደረገው፡፡ የሟቹን
ኮት ካወለቀ በኋላ የሚደሙትን ቀዳዳዎች ለተመልካች አሳየ።
«ይሄ ነው ባንዲራችን!»
ነጭ አንሶላ አምጥተው የመሴይ ማብዩፍን አስከሬን ሸፈኑት:: ስድስት ሰዎች ጠብመንጃዎቻቸውን ከስር አጋድመው ሬሣውን ከዚያ ላይ ካሳረፉ በኋላ ወደ ምድር ቤት በዝግታ ወስደው ከትልቅ ጠረጴዛ ላይ አጋደሙት፡፡ ሰዎቹ በሚፈጽሙት ተግባር ቅዱስነት በመዋጥ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ
መሆናቸውን ጨርሰው ረሱ::
አስከሬኑ ከዣቬር ከታሰረበት ግንድ አጠገብ ሲያልፍ ኢንጆልራስ
ሰላዩን አናገረው::
«የምትቀጥለው አንተ ነህ::»
በዚህ ጊዜ ብቻውን የጥበቃውን ተግባር ያከናውን የነበረው ጋብሮች ሰዎች ከምሽጉ ውስጥ ሲገቡ ውልብ አለው:: በድንገት ጩኸት ተሰማ::
‹‹ተጠንቀቁ!»
የአድማው መሪዎች በሙሉ ዘልለው ወደ ውጭ ወጡ:: የሚያባክኑት ጊዜ አልነበራቸውም:: ወታደሮች ሳንጃቸውን ወድረው ከምሽጉ ሲገቡ ተመለከቱ፡፡
ያቺ ሰዓት ወሳኝ ነበረች:: ምሽጉ በንጉሡ ወታደሮች ተወረረ::
በመጀመሪያ ዘልሎ የገባው ወታደር ከውስጥ የነበረ አንድ ሰው ግምባሩን ብሎ ጣለው:: ገዳዩ ወዲያው በጠላት ወገን ወታደር ተገደለ:: አሁንም ሌላ
ወታደር ከርፌይራክን ከመሬት ስለዘረረው እንደወደቀ «እርዱኝ» እያለ ጮኸ፡፡ በዚያው ወቅት እጅግ በጣም ግዙፍ የሆነ ወታደር ጋቭሮች ከነበረበት ክፍል ገባ፡፡ ጋቭሮች ጠብመንጃዋን ከዣቬር ወደ ወታደሩ አዙራ ለመተኮስ
ቶሎ ብላ ቃታውን ሳብ አደረገች:: ግን ምን ይሆናል ዣቬር ጠብመንጃውን ሲሰጥ ለካስ ጥይት አላጎረሰው ኖር ፀጥ አለ፡፡ ወታደሩ ከት ብሎ ሳቀ፡፡
ሳንጃውን ወድሮ ወደ ልጁ ሄደ::
ወታደሩ ልጁ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ከኋላው ስለተመታ በአፍጢሙ ተደፋ:: ወዲያው ከርፌይራክን የመታው ወታደር ሲወድቅ ታየ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የገደላቸወ ማሪየስ ነበር፡፡
ማሪየስ የመጀመሪያውን ውጊያ በሩቁ ሆኖ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ
ነበር ያየው:: በሁለተኛው ግን የጋብሮችን ሕይወት በመጀመሪያ ሲያድን ጓደኛውን ቀጥሎ ነው ነፃ ያወጣው፡፡ ኩርፌይራክ ከመሬት ወደቀ እንጂ አልተመታም ነበር፡፡
ወታደሮቹ ከምሽጉ ሁለት ሦስተኛ የሚሆነውን ክፍል ከቁጥጥራቸው
ሥር አውለዋል፡፡ በጣም ወደ ውስጥ ዘልቀው ለመግባት ግን አልደፈሩም:: ምናልባት አንድ ዓይነት ወጥመድ ቢኖር ብለው ተጠራጥረዋል። በዚያ !
አካባቢ ይበራ የነበረው መብራት እስከ ውስጥ ዘልቆ አያሳይም::
አንድ ወታደር ማሪየስን ለመጣል ሲያነጣጥር ድንገት ከመሀል አንድ ሰው በመግባቱ የእርሱን እጣ ሰውዬው ወሰደ:: ወዲያው በድንገት አንድ በጣም የሚጮህ ድምፅ ተሰማ::
«እጃችሁን ስጡ ፤ አለበለዚያ ምሽጉን እንዳለ እናቃጥለዋለን፡፡»
አድምኞቹ ሁሉ ድምፁ ወደ ተሰማበት አቅጣጫ ፊታቸውን አዞሩ፡፡ ማሪየስ ከየት መጣ ሳይባል ይህን ያለውን የሃምሣ አለቃ ስለጣለው ምሽጉ ከመጥፋት ዳነ፡፡
አድመኞቹ በሙሉ ማሪየስን ከበቡት:: ኩርፌይራክ ከወደቀበት ተነስቶ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመ
«እንዴት ያለ አጋጣሚ ነው» አለ ኮምብፌሬ::
«ጥሩ ጊዜ ደረስክ» አለ ቦስዩ ቀጠለና::
«አንተ ባትደርስ ይህን ጊዜ በሕይወት የለሁም» አለ ከርፌይራክ።
«እኔ ደግሞ ይህን ጊዜ በአፍጢሜ ተደፍቼ ነበር» አለ ጋቭሮች ቀጥሎ፡፡
ወዲያው አንድ ድርጊት በመፈጸሙ ደስታቸው በሀዘን ተለወጠ። ከመካከላቸው በጣም የሚወዱትና የሚያደንቁት አንዱ ጓደኛቸው ተሰወረ። ከቁስለኛ መካከል ፈለጉት:: ከዚያ አልነበረም:: ከሞቱት መካከል አዩት ከዚያም አልነበረም፡፡ ተማርኳል ማለት ነበር፡፡
«ወንድማችንን ወሰዱት፤ እኛ የእነርሱን መኮንን እንደያዝን ሁሉ
እነርሱም ጓደኛችንን ያዙት ማለት ነው:: በሰላዩ ላይ ስለምንወስደው
እርምጃ ወስነናል?» ሲል ኮምብፌሬ ኢንጆልራስን ጠየቀው፡፡
«አዎን» አለ ኢንጆልራስ የኮምብፌሬን ትከሻ እየነካካ፡፡ «ሆኖም የሰላዩ ደም የጓደኛችንን የዣን ጥሩቬርንን ደም አያህልም፡፡»
«እንግዲያውማ» አለ ኮምብፌራ «መሐረቤን ከጠመንጃዬ ጫፍ
አስሬ ልውጣና ሰላዩን በጓደኛችን እንዲለወጡን ልጠይቅ::»
«ስማ» ብሎ ኢንጆልራስ ሲናገር ከውጭ አንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
የወንድ ድምፅ ነበር::
«ፈረንሣይ ለዘላለም ትኑር!»
የጓደኛቸው ድምዕ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጥይት ተተኩሰ፡፡ ከዚያም ሁሉም ነገር እርጭ አለ::
«ጓደኛችንን ገደሉት!» አለ ኮምብፌሬ:: ኢንጆልራስ ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ጓደኞችህ አሁን አንተን ነው የገደሉት» አለው::
አድመኞቹ ሁሉ አሁን ከቤት ወስጥ ገብቷል:: ማሪየስም
ተከትሉኣቸው ሊገባ ሲል «መሴይ ማሪየስ» ተብሎ ስሙ ሲጠራ ሰምቶ በመደንገጥ ዞር አለ፡፡ ከሁለት ሰዓት በፊት ኮዜትን እየጠበቀ ሳለ ከአጥር ውጭ ሆኖ የጠራው ድምፅ እንደሆነ አውቋል፡፡ ማን እንደሆነ ለማወቅ
ፊቱን ቢያዞርም መለየት አልቻለም:: «እዚህ ነኝ» አለ ያው ድምፅ በጣም የደከመ በመምሰል፡፡
መሬት ለመሬት እየተንፏቀቀ የሚመጣ ሰው በሩቁ ተመለከተ፡፡
መብራት ካለበት ሲደርስ የሴት ሸሚዝ የለበሰ ሰው መሆኑን አየ:: ከስር የተቀዳደደ ሱሪ ታጥቋል፡፡ ጫማ አላጠለቀም፡፡ ይህ ፍጡር ማሪየስ ከነበረበት ሲደርስ የገረጣ ፊቱን ቀና አደረገ፡፡
«አታውቀኝም?»
«የለም»
«ኢፓኒን፡፡»
ማሪየስ ቶሎ ብሎ ወደ መሬት አጎነበሰ፡፡ እውነትም ያቺ እድለቢስ
ኢፖኒን ነበረች፡፡ እንደ ወንድ ነው የለበሰችው::
«እንዴት መጣሽ?» ከዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?
‹‹መሞቴ ነው» ስትል መለሰችለት::
ማሪየስ ደንግጦ «ተመትተሻል እንዴ?» ሲል ጠየቃት::
ከመሬት ብድግ ሊያደርጋት ቀኝ እጁን ከወገብዋ ስር አስገባ፡፡ ብድግ ሲያደርጋት እጅዋ ተዝለፈለፈ:: የማቃሰት ድምፅ አሰማች፡፡
«አሳመምኩሽ?»
«ትንሽ»
«ምነው እጅሽ ዛለ?» ብሎ" ሲያየው በጥይት ተመትቷል፡፡
«ቆስሎአል፧ አይደለም?»
«አዎን፡፡»
«ማን መታሽ?»
«ከጥቂት ጊዜ በፊት ጠብመንጃ ተደቅኖብህ ልትመታ ስትል አንድ
ሰው ከመሀል መግባቱ ትዝ ይልሃል?»
«አዎን፣ አስታውሳለሁ::»
የእኔ እጅ ነው ጣልቃ የገባው::
የማሪየስ ልብ ከሁለት የተሰነጠቀ መሰለው:: ነገሩ አልገባውም::
ምነው እንደዚያ አደረግሽ! ምስኪን! ብቻ ቁስሉ ለክፉ አይሰጥሽም።
ለማንኛውም ከውስጥ አስገብቼ ላስተኛሽ፡፡»
እጄ ብቻ እኮ አይደለም የተመታው:: ጥይቱ በእጄ አልፎ ከብብቴ ጥቂት ዝቅ ብሉ ወደ ወገቤ በመግባቱ ቀስፎ ይዞኛል» አለች በኃይል ለመተንፈስ እየታገለች::
«ስለዚህ ወደ ውስጥ መግባቱ ዋጋ የለውም:: አሁን ብቻ ከአጠገቤ ቁጭ ብለህ አጫውተኝ፡፡ ጨዋታህ ከሐኪም እርዳታ ይበልጥብኛል፡፡»
ትእዛዝዋን ተቀብሎ እግሩን በመዘርጋት ከአጠገብዋ ቁጭ አለ።
ጭንቅላትዋን ከጉልበቱ ላይ አሳረፈች:: ቀና ብላ ሳታየው «እፎይ ተመስገን እንዴት ይመቻል? ምን ዓይነት ደግ ሰው ነህ! በቃ! ሕመሙ ተቀነሰልኝ
ስትል ቀባጠረች፣::
ከዚያም ለጥቂት ጊዜ ፀጥ አለች:: ቀስ ብላ ፊትዋን ወደ ማሪየስ
አዙራ ቀና ብላ አየችው::
«አስቀያሚ ናት ነው ያልከው፤ አይደል? » ንግግርዋን በማቆም ጥቂት ዝም ካለች በኋላ እንደገና ቀጠለች::
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ኢንጆልራስ ጎንበስ ብሎ የራሣውን ጭንቅላት ቀና ካደረገ በኋላ ግምባሩን ሳመው፡፡
መሞቱን በመርሳት በጥንቃቄ ያልያዘው እንደሆነ የሚያምመው ይመስል ቀስ ብሎ በክርኑ ደግፎ ቀና አደረገው፡፡ የሟቹን
ኮት ካወለቀ በኋላ የሚደሙትን ቀዳዳዎች ለተመልካች አሳየ።
«ይሄ ነው ባንዲራችን!»
ነጭ አንሶላ አምጥተው የመሴይ ማብዩፍን አስከሬን ሸፈኑት:: ስድስት ሰዎች ጠብመንጃዎቻቸውን ከስር አጋድመው ሬሣውን ከዚያ ላይ ካሳረፉ በኋላ ወደ ምድር ቤት በዝግታ ወስደው ከትልቅ ጠረጴዛ ላይ አጋደሙት፡፡ ሰዎቹ በሚፈጽሙት ተግባር ቅዱስነት በመዋጥ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ
መሆናቸውን ጨርሰው ረሱ::
አስከሬኑ ከዣቬር ከታሰረበት ግንድ አጠገብ ሲያልፍ ኢንጆልራስ
ሰላዩን አናገረው::
«የምትቀጥለው አንተ ነህ::»
በዚህ ጊዜ ብቻውን የጥበቃውን ተግባር ያከናውን የነበረው ጋብሮች ሰዎች ከምሽጉ ውስጥ ሲገቡ ውልብ አለው:: በድንገት ጩኸት ተሰማ::
‹‹ተጠንቀቁ!»
የአድማው መሪዎች በሙሉ ዘልለው ወደ ውጭ ወጡ:: የሚያባክኑት ጊዜ አልነበራቸውም:: ወታደሮች ሳንጃቸውን ወድረው ከምሽጉ ሲገቡ ተመለከቱ፡፡
ያቺ ሰዓት ወሳኝ ነበረች:: ምሽጉ በንጉሡ ወታደሮች ተወረረ::
በመጀመሪያ ዘልሎ የገባው ወታደር ከውስጥ የነበረ አንድ ሰው ግምባሩን ብሎ ጣለው:: ገዳዩ ወዲያው በጠላት ወገን ወታደር ተገደለ:: አሁንም ሌላ
ወታደር ከርፌይራክን ከመሬት ስለዘረረው እንደወደቀ «እርዱኝ» እያለ ጮኸ፡፡ በዚያው ወቅት እጅግ በጣም ግዙፍ የሆነ ወታደር ጋቭሮች ከነበረበት ክፍል ገባ፡፡ ጋቭሮች ጠብመንጃዋን ከዣቬር ወደ ወታደሩ አዙራ ለመተኮስ
ቶሎ ብላ ቃታውን ሳብ አደረገች:: ግን ምን ይሆናል ዣቬር ጠብመንጃውን ሲሰጥ ለካስ ጥይት አላጎረሰው ኖር ፀጥ አለ፡፡ ወታደሩ ከት ብሎ ሳቀ፡፡
ሳንጃውን ወድሮ ወደ ልጁ ሄደ::
ወታደሩ ልጁ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ከኋላው ስለተመታ በአፍጢሙ ተደፋ:: ወዲያው ከርፌይራክን የመታው ወታደር ሲወድቅ ታየ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የገደላቸወ ማሪየስ ነበር፡፡
ማሪየስ የመጀመሪያውን ውጊያ በሩቁ ሆኖ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ
ነበር ያየው:: በሁለተኛው ግን የጋብሮችን ሕይወት በመጀመሪያ ሲያድን ጓደኛውን ቀጥሎ ነው ነፃ ያወጣው፡፡ ኩርፌይራክ ከመሬት ወደቀ እንጂ አልተመታም ነበር፡፡
ወታደሮቹ ከምሽጉ ሁለት ሦስተኛ የሚሆነውን ክፍል ከቁጥጥራቸው
ሥር አውለዋል፡፡ በጣም ወደ ውስጥ ዘልቀው ለመግባት ግን አልደፈሩም:: ምናልባት አንድ ዓይነት ወጥመድ ቢኖር ብለው ተጠራጥረዋል። በዚያ !
አካባቢ ይበራ የነበረው መብራት እስከ ውስጥ ዘልቆ አያሳይም::
አንድ ወታደር ማሪየስን ለመጣል ሲያነጣጥር ድንገት ከመሀል አንድ ሰው በመግባቱ የእርሱን እጣ ሰውዬው ወሰደ:: ወዲያው በድንገት አንድ በጣም የሚጮህ ድምፅ ተሰማ::
«እጃችሁን ስጡ ፤ አለበለዚያ ምሽጉን እንዳለ እናቃጥለዋለን፡፡»
አድምኞቹ ሁሉ ድምፁ ወደ ተሰማበት አቅጣጫ ፊታቸውን አዞሩ፡፡ ማሪየስ ከየት መጣ ሳይባል ይህን ያለውን የሃምሣ አለቃ ስለጣለው ምሽጉ ከመጥፋት ዳነ፡፡
አድመኞቹ በሙሉ ማሪየስን ከበቡት:: ኩርፌይራክ ከወደቀበት ተነስቶ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመ
«እንዴት ያለ አጋጣሚ ነው» አለ ኮምብፌሬ::
«ጥሩ ጊዜ ደረስክ» አለ ቦስዩ ቀጠለና::
«አንተ ባትደርስ ይህን ጊዜ በሕይወት የለሁም» አለ ከርፌይራክ።
«እኔ ደግሞ ይህን ጊዜ በአፍጢሜ ተደፍቼ ነበር» አለ ጋቭሮች ቀጥሎ፡፡
ወዲያው አንድ ድርጊት በመፈጸሙ ደስታቸው በሀዘን ተለወጠ። ከመካከላቸው በጣም የሚወዱትና የሚያደንቁት አንዱ ጓደኛቸው ተሰወረ። ከቁስለኛ መካከል ፈለጉት:: ከዚያ አልነበረም:: ከሞቱት መካከል አዩት ከዚያም አልነበረም፡፡ ተማርኳል ማለት ነበር፡፡
«ወንድማችንን ወሰዱት፤ እኛ የእነርሱን መኮንን እንደያዝን ሁሉ
እነርሱም ጓደኛችንን ያዙት ማለት ነው:: በሰላዩ ላይ ስለምንወስደው
እርምጃ ወስነናል?» ሲል ኮምብፌሬ ኢንጆልራስን ጠየቀው፡፡
«አዎን» አለ ኢንጆልራስ የኮምብፌሬን ትከሻ እየነካካ፡፡ «ሆኖም የሰላዩ ደም የጓደኛችንን የዣን ጥሩቬርንን ደም አያህልም፡፡»
«እንግዲያውማ» አለ ኮምብፌራ «መሐረቤን ከጠመንጃዬ ጫፍ
አስሬ ልውጣና ሰላዩን በጓደኛችን እንዲለወጡን ልጠይቅ::»
«ስማ» ብሎ ኢንጆልራስ ሲናገር ከውጭ አንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
የወንድ ድምፅ ነበር::
«ፈረንሣይ ለዘላለም ትኑር!»
የጓደኛቸው ድምዕ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጥይት ተተኩሰ፡፡ ከዚያም ሁሉም ነገር እርጭ አለ::
«ጓደኛችንን ገደሉት!» አለ ኮምብፌሬ:: ኢንጆልራስ ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ጓደኞችህ አሁን አንተን ነው የገደሉት» አለው::
አድመኞቹ ሁሉ አሁን ከቤት ወስጥ ገብቷል:: ማሪየስም
ተከትሉኣቸው ሊገባ ሲል «መሴይ ማሪየስ» ተብሎ ስሙ ሲጠራ ሰምቶ በመደንገጥ ዞር አለ፡፡ ከሁለት ሰዓት በፊት ኮዜትን እየጠበቀ ሳለ ከአጥር ውጭ ሆኖ የጠራው ድምፅ እንደሆነ አውቋል፡፡ ማን እንደሆነ ለማወቅ
ፊቱን ቢያዞርም መለየት አልቻለም:: «እዚህ ነኝ» አለ ያው ድምፅ በጣም የደከመ በመምሰል፡፡
መሬት ለመሬት እየተንፏቀቀ የሚመጣ ሰው በሩቁ ተመለከተ፡፡
መብራት ካለበት ሲደርስ የሴት ሸሚዝ የለበሰ ሰው መሆኑን አየ:: ከስር የተቀዳደደ ሱሪ ታጥቋል፡፡ ጫማ አላጠለቀም፡፡ ይህ ፍጡር ማሪየስ ከነበረበት ሲደርስ የገረጣ ፊቱን ቀና አደረገ፡፡
«አታውቀኝም?»
«የለም»
«ኢፓኒን፡፡»
ማሪየስ ቶሎ ብሎ ወደ መሬት አጎነበሰ፡፡ እውነትም ያቺ እድለቢስ
ኢፖኒን ነበረች፡፡ እንደ ወንድ ነው የለበሰችው::
«እንዴት መጣሽ?» ከዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?
‹‹መሞቴ ነው» ስትል መለሰችለት::
ማሪየስ ደንግጦ «ተመትተሻል እንዴ?» ሲል ጠየቃት::
ከመሬት ብድግ ሊያደርጋት ቀኝ እጁን ከወገብዋ ስር አስገባ፡፡ ብድግ ሲያደርጋት እጅዋ ተዝለፈለፈ:: የማቃሰት ድምፅ አሰማች፡፡
«አሳመምኩሽ?»
«ትንሽ»
«ምነው እጅሽ ዛለ?» ብሎ" ሲያየው በጥይት ተመትቷል፡፡
«ቆስሎአል፧ አይደለም?»
«አዎን፡፡»
«ማን መታሽ?»
«ከጥቂት ጊዜ በፊት ጠብመንጃ ተደቅኖብህ ልትመታ ስትል አንድ
ሰው ከመሀል መግባቱ ትዝ ይልሃል?»
«አዎን፣ አስታውሳለሁ::»
የእኔ እጅ ነው ጣልቃ የገባው::
የማሪየስ ልብ ከሁለት የተሰነጠቀ መሰለው:: ነገሩ አልገባውም::
ምነው እንደዚያ አደረግሽ! ምስኪን! ብቻ ቁስሉ ለክፉ አይሰጥሽም።
ለማንኛውም ከውስጥ አስገብቼ ላስተኛሽ፡፡»
እጄ ብቻ እኮ አይደለም የተመታው:: ጥይቱ በእጄ አልፎ ከብብቴ ጥቂት ዝቅ ብሉ ወደ ወገቤ በመግባቱ ቀስፎ ይዞኛል» አለች በኃይል ለመተንፈስ እየታገለች::
«ስለዚህ ወደ ውስጥ መግባቱ ዋጋ የለውም:: አሁን ብቻ ከአጠገቤ ቁጭ ብለህ አጫውተኝ፡፡ ጨዋታህ ከሐኪም እርዳታ ይበልጥብኛል፡፡»
ትእዛዝዋን ተቀብሎ እግሩን በመዘርጋት ከአጠገብዋ ቁጭ አለ።
ጭንቅላትዋን ከጉልበቱ ላይ አሳረፈች:: ቀና ብላ ሳታየው «እፎይ ተመስገን እንዴት ይመቻል? ምን ዓይነት ደግ ሰው ነህ! በቃ! ሕመሙ ተቀነሰልኝ
ስትል ቀባጠረች፣::
ከዚያም ለጥቂት ጊዜ ፀጥ አለች:: ቀስ ብላ ፊትዋን ወደ ማሪየስ
አዙራ ቀና ብላ አየችው::
«አስቀያሚ ናት ነው ያልከው፤ አይደል? » ንግግርዋን በማቆም ጥቂት ዝም ካለች በኋላ እንደገና ቀጠለች::
👍19
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የልጅትዋ አድራሻ
ኮዜት ቀኑን ሙሉ እህል በአፍዋ ሳይገባ ከክፍልዋ ውስጥ ተዘግታ
ዋለች፡፡ መሄጃቸው ስለተቃረበ ያንን የነበሩበትን ትልቅ ቤት ለቅቀው ሆቴል ቤት ነበር የገቡት:: ያን እለት የዣን ቫልዥ የመብላት ፍላጎት ከመቼውም ይበልጥ ስለተከፈተ እራቱን በጊዜ እንክት አድርጎ ይበላል።
ኮዜት ከማዕዱ አልቀረበችም፡፡ እራቱን እየበላ ሳለ ሠራተኛው ከአንዴም ሁለቴ፣ ከሁለቴ ሦስቴ ብቅ ጥልቅ እያለች «ኧረ እኔ አላማረኝም፤ አገሩ ተረብሿል፧ ውጊያው ተጧጡፏል አሉ» በማለት ስታናግረው መንፈሱ
ጥቂት ይሽበራል፡፡ ሆኖም እስከዚህም ስሜት አልሰጠውም:: ኮዜትን ይዞ ወደ እንግሊዝ አገር ከሄደ ከዚያ ደስ ብሎት ሊኖር እንደሚችል ያሰላስላል።
ከነበረበት ብድግ ብሎ ነበር ወደ መስኮት፧ ከመስኮት ወደ በር በአሳብ ተውጦ ሲንቆራጠጥ አንድ ነገር አየ፡፡
ተሰቅሎ ከነበረው መስታወት አጠገብ አንድ ጽሑፍ ሳይተጣጠፍ
ከመሬት ወድቆ ስለነበር በመስታወቱ አንጸባራቂነት ከውስጥ በኩል አየው፡፡
ጽሑፉም እንዲህ ይላል፡፡
የእኔ ፍቅር! የሚገርምህ ነው፤ አባዬ አሁኑኑ እንድንሄድ ይፈልጋል፡
ዛሬ ማታ ሆም አርሜ ከተባለ ሥፍራ እንሄዳለን:: በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ከእንግሊዝ አገር እንገባለን፡፡ ኮዜት ሰኔ 4»
ዣን ቫልዣ ፈዝዞ ቀረ::
ኮዜት ሀዘን በዝቶባት ስለነበር ለማሪየስ የላከችውን ደብዳቤ ረቂቅ ጽሑፉን ከጻፈችበት ሥፍራ ረስታዋለች::
ዣን ቫልዣ ወደ መስታወቱ ጠጋ ብሎ ጽሑፉን እንደገና አነበበው::
ማመን አቃተው፡፡ ከኮዜት የተለየ መሰለው:: «ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?» ሲል ጭንቀት ያዘው:: ጎንበስ ብሎ ጽሑፉን አነሳው:: በጣም ተረበሸ፡፡ ዓለም ጨለመችበት:: መቼስ በሕይወት ሊደርስ ከሚችል ማንኛውም
አሲቃቂ ነገር ሁሉ የወደዱትን ከማጣት ይበልጥ የሚያንገበግብ፣ የሚያሳርር
ነገር የለም:: ዣን ቫልዣ ያንን ጽሑፍ በማንበቡ ያቺን የሚወዳትንና ብቸኝነቱን የሚረሳባትን ኮዜት ያጣ መሰለው:: ከአሁን በፊት እንደጠቀስነው ዣን ቫልዣ ኮዜትን እንደ ልጅ ብቻ ኣልነበረም የሚያያት:: ኮዜት ለእርሱ
እንደ ልጅም፣ እንደ እህትም፣ እንደ እናትም ነበረች:: ሕይወትን ጠልቶ ሳለ ሕይወትን መልሶ እንዲያፈቅር ያደረገችው ኮዚት ናት:: ዣን ቫልዣ
ፍቅረኛ ወይም ሚስት አልነበረውም:: ስለዚህ የፍቅሩ ጽናት የሰፈረው ኮዜት ላይ ነበር ለማለት ይቻላል:: በአባትነቱ እርስዋም ከልብ ትወደዋለች::
ያ ፍቅር አክትሞ በሌላ የተተካ ስለመሰለው ነበር እንደዚያ እጢው ዱብ እስኪል የደነገጠው:: ሌላ ማስረጃ የሚያሻው ነገር አይደለም፡፡ ወረቀቱ ከፊቱ ላይ ነው ያለው:: «ፍቅረኛ አላት ማለት ነው ፤ መሄድዋ ነው እንግዲህ» ሲል አጉረመረመ:: የብቸኝነት ስሜት ወረረው:: «እኔን እንደጎበያ
ድንጋይ ጎልታ ልትሄድ! » ለእኔ የሚለው የራስ ወዳድነት ስሜት
ተጠናወተው:: ልቡ የተቃውሞ ኃይል አረገዘ:: ዣን ቫልዣ ይህን እያሰላሰለ ሳለ ሠሪተኛዋ እርሱ ከነበረበት ክፍል ገባች::
«ውጊያ ይካሄዳል ያለሽው የት ሰፈር ነበር? ቦታውን አውቀሽዋል?»
ሠራተኛዋ ተገርማ «እርስዎ ከፈለጉ ምን ገድዶኝ እነግሮታለሁ» ስትል መለሰች::
«ውጊ.ያው ተጧጡፎአል ብለሽ አሁን አልነገርሽኝም እንዴ!» በማለት ቀጠለ::
«አዎን ጌታዬ!›› አለች ሠራተኛዋ ፤ ከዚያ ከማርያም ቤተ ክርስቲያን
ባሻገር ነው:: ››
ዣን ቫልዣ ከነበረበት ውጭ ወጥቶ ደንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡
ጊዜው ጨልሞአል::
ውርጭ ላይ ለምን ያህል ሰዓት ተቀመጠ? እግሩን በመዘርጋትና
በማጣጠፍ ራሱን አዝናና ወይስ ኩርምት ብሎ ነው የቀረው? እንዳጎነበሰ ቀረ ወይስ ቀና አለ? አንድ ነገር ተደግፎ ነው ወይስ እንዲሁ ጉች ብሎ ነው
የተቀመጠው? ራሱ እንኳን ቢሆን ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ሊሰጥ አይችልም።
በአንድ ወቅት የኮቴ ድምፅ ስለሰማ ብቻ ቀና አለ፡፡ አንድ ልጅ ወደ እርሱ ሲመጣ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮች መልእክቱን ለማድረስ ከቤቱ ደረሰ። ወደ ላይ እያየ የቤት ቁጥር ሲፈልግ ዣን ቫልዣ አየው:: ሆኖም ከቁጥር አላስገባውም::
«አንተ ልጅ» አለ ዣን ቫልዣ ፧
«ምን ሆነሃል?»
«የሆንኩትማ እርቦኛል» ሲል ጋቭሮች በድፍረት መለሰለት:: ምናምን ይሰጡኛል?» አለ ቀጠለና፡፡
ዣን ቫልዣ ከኪሱ አንድ መቶ ሱስ አወጣና ሰጠው::
ግን ጋቭሮች አደብ የሌለው ተቅበጥባጭ ልጅ እንደመሆኑ መጠን ገንዘቡን እንደ መቀበል ድንጋይ አነሳ፡፡ የሚሰራ የመንገድ መብራት አየ::
«አሁንም የውጭ መብራት ታበራላችሁ እንዴ?» ሲል ጋቭሮች
ጠየቀ፡፡ «በአሁኑ ጊዜ እኮ መብራት ማብራት ጥሩ አይደለም» ካለ በኋላ
ድንጋዩን ወርውሮ መብራቱን ሰበረው፡፡ አካባቢው በድንገት ጨለመ::
ዣን ቫልዣ ወደ ልጁ ተጠጋ::
«ወይ ምስኪን፣ እንዲህ የሚያስደርገው ምናልባት ረሃቡ ይሆናል። ሲል እርስ በራሱ ተነጋገረ፡፡ መቶውን ሱስ አስጨበጠው::
ጋብሮች የምንተ እፍረቱን ገንዘቡን ተቀበለ፡፡
«ሌላ መብራት እንዳልሰብር ነው» አለ እንዳቀረቀረ፡፡
«እንደ ፈለግህ ስበር፧ እኔ ምን አገባኝ» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት።
«ጥሩ ሰው ነዎት!» አለ ጋቭሮች::
አምስቱን ፍራንክ ማለት አንድ መቶ ሱስ ከኪሱ ውስጥ ጨመረ።
ሰውዬውን ስለወደደው በድፍረት ጥያቄ ጠየቀው::
«የዚሁ ሰፈር ሰው ነዎት?»
«ምን ፈለግህ?»
«የቤት ቁጥር 7 የትኛው እንደሆነ ያሳዩኛል?»
«ከዚያ ምን አለህ?»
እዚህ ላይ ልጁ አመነታ:: ሰውዩውን ያስቀየመው መስለው:: ፀጉሩን በጥፍሩ ያክ ጀመር፡፡
«ብቻ» በማለት የያዘውን ደብዳቤ አሳየው::
ዣን ቫልዣ በድንገት አንድ ሀሳብ ስለመጣለት «ስጠብቀው የነበረውን ደብዳቤ አመጣህልኝ» አለው::
«ለእርስዎ?» ሲል ጋቭሮች ጠየቀ፡፡ «እርስዎ ሴት አይደሉ!»
«ደብዳቤው ለወ/ት ኮዜት ነው፤ አይደለም?»
«ኮዜት?» ሲል ጋቭሮች አጉረመረመ:: «አዎን ደብዳቤው የእርሳቸው ነው ፤ ስማቸው ግን ያስቃል፡፡»
«ይሁን ግድ የለም» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «ደብዳቤውን እኔ እሰጣታለሁና
ለእኔ ስጠኝ፡፡»
«እንግዲያውስ ውጊያው ከሚካሄድበት ቦታ እንደመጣ እንዲነግሯት እፈልጋለሁ::»
«ጥሩ» አለ ዣን ቫልዣ::
ጋቭሮች ደብዳቤውን ከሰጠው በኋላ ለዣን ቫልዣ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠው::
«ደብዳቤውን በጥንቃቄ ይያዙት ፤ ከአስተዳደር ነው የመጣው::
እርስዎም ይቸኩላሉ እንዴ? ለመሆኑ ደብዳቤውን የተቀበለው ማነው እላለሁ? ስምዎን ይንገሩኛ ደብዳቤውን ለላኩት እመቤት እንድነግር» ሲል
ኩራት እየተሰማው ተናገረ፡፡
‹‹ጥያቄውን የሚያቀርቡት ቅድስት ፍንዱቄ ናቸው?» ሲል ዣን
ቫልዣ ጠየቀው::
«ቸኩያለሁ፤ ደብዳቤውን ያመጣሁት ከውጊያ ሥፍራ ነው፤ አሁንም ወደዚያው መመለሴ ነው» ብሎ መንገዱን በመቀጠል ሰፈር እንደጠፋበት ወፍ በርሮ ሄደ::
ዣን ቫልዣ ማሪየስ የጻፈውን ደብዳቤ ይዞ ወደ ውስጥ ገባ፡፡ ከክፍሉ ውስጥ ገብቶ በሩን ከዘጋ በኋላ ጥምብ እንዳገኘ አሞራ በመቸኵል ደብዳቤውን
ገለጠው:: የታየሁ እንደሆነ ብሎ በመፍራት ቀና አለና ዙሪያውን ተመለከተ፡፡
ማንም የለም:: ኮዜትና ሠራተኛዋ ተኝተዋል ሲል ግምት ወሰደ::
የሚያደርገው ነገር የሌብነት ስለሆነ ሻማ ለመለኮስ ክብሪት ሲጭር እጁ ተንቀጥቅጦበት ነበር፡፡ አሁን ግን ትንሽ መንፈሱ ስለተረጋጋ ሻማውን አቀጣጠለ፡፡ ከጠረጴዛ ላይ ክርኑን አስደግፎ ደብዳቤውን ማንበብ ጀመረ::
ማሪየስ ለኮዜት ከጻፈው ደብዳቤ ውስጥ የሚከተሉትን ቃላት ብቻ
አጤነ፡፡
«እሞታለሁ፤ ይህን ደብዳቤ ስታነቢ ነፍሴ ከአጠገብሽ ይሆናል፡፡»
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የልጅትዋ አድራሻ
ኮዜት ቀኑን ሙሉ እህል በአፍዋ ሳይገባ ከክፍልዋ ውስጥ ተዘግታ
ዋለች፡፡ መሄጃቸው ስለተቃረበ ያንን የነበሩበትን ትልቅ ቤት ለቅቀው ሆቴል ቤት ነበር የገቡት:: ያን እለት የዣን ቫልዥ የመብላት ፍላጎት ከመቼውም ይበልጥ ስለተከፈተ እራቱን በጊዜ እንክት አድርጎ ይበላል።
ኮዜት ከማዕዱ አልቀረበችም፡፡ እራቱን እየበላ ሳለ ሠራተኛው ከአንዴም ሁለቴ፣ ከሁለቴ ሦስቴ ብቅ ጥልቅ እያለች «ኧረ እኔ አላማረኝም፤ አገሩ ተረብሿል፧ ውጊያው ተጧጡፏል አሉ» በማለት ስታናግረው መንፈሱ
ጥቂት ይሽበራል፡፡ ሆኖም እስከዚህም ስሜት አልሰጠውም:: ኮዜትን ይዞ ወደ እንግሊዝ አገር ከሄደ ከዚያ ደስ ብሎት ሊኖር እንደሚችል ያሰላስላል።
ከነበረበት ብድግ ብሎ ነበር ወደ መስኮት፧ ከመስኮት ወደ በር በአሳብ ተውጦ ሲንቆራጠጥ አንድ ነገር አየ፡፡
ተሰቅሎ ከነበረው መስታወት አጠገብ አንድ ጽሑፍ ሳይተጣጠፍ
ከመሬት ወድቆ ስለነበር በመስታወቱ አንጸባራቂነት ከውስጥ በኩል አየው፡፡
ጽሑፉም እንዲህ ይላል፡፡
የእኔ ፍቅር! የሚገርምህ ነው፤ አባዬ አሁኑኑ እንድንሄድ ይፈልጋል፡
ዛሬ ማታ ሆም አርሜ ከተባለ ሥፍራ እንሄዳለን:: በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ከእንግሊዝ አገር እንገባለን፡፡ ኮዜት ሰኔ 4»
ዣን ቫልዣ ፈዝዞ ቀረ::
ኮዜት ሀዘን በዝቶባት ስለነበር ለማሪየስ የላከችውን ደብዳቤ ረቂቅ ጽሑፉን ከጻፈችበት ሥፍራ ረስታዋለች::
ዣን ቫልዣ ወደ መስታወቱ ጠጋ ብሎ ጽሑፉን እንደገና አነበበው::
ማመን አቃተው፡፡ ከኮዜት የተለየ መሰለው:: «ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል?» ሲል ጭንቀት ያዘው:: ጎንበስ ብሎ ጽሑፉን አነሳው:: በጣም ተረበሸ፡፡ ዓለም ጨለመችበት:: መቼስ በሕይወት ሊደርስ ከሚችል ማንኛውም
አሲቃቂ ነገር ሁሉ የወደዱትን ከማጣት ይበልጥ የሚያንገበግብ፣ የሚያሳርር
ነገር የለም:: ዣን ቫልዣ ያንን ጽሑፍ በማንበቡ ያቺን የሚወዳትንና ብቸኝነቱን የሚረሳባትን ኮዜት ያጣ መሰለው:: ከአሁን በፊት እንደጠቀስነው ዣን ቫልዣ ኮዜትን እንደ ልጅ ብቻ ኣልነበረም የሚያያት:: ኮዜት ለእርሱ
እንደ ልጅም፣ እንደ እህትም፣ እንደ እናትም ነበረች:: ሕይወትን ጠልቶ ሳለ ሕይወትን መልሶ እንዲያፈቅር ያደረገችው ኮዚት ናት:: ዣን ቫልዣ
ፍቅረኛ ወይም ሚስት አልነበረውም:: ስለዚህ የፍቅሩ ጽናት የሰፈረው ኮዜት ላይ ነበር ለማለት ይቻላል:: በአባትነቱ እርስዋም ከልብ ትወደዋለች::
ያ ፍቅር አክትሞ በሌላ የተተካ ስለመሰለው ነበር እንደዚያ እጢው ዱብ እስኪል የደነገጠው:: ሌላ ማስረጃ የሚያሻው ነገር አይደለም፡፡ ወረቀቱ ከፊቱ ላይ ነው ያለው:: «ፍቅረኛ አላት ማለት ነው ፤ መሄድዋ ነው እንግዲህ» ሲል አጉረመረመ:: የብቸኝነት ስሜት ወረረው:: «እኔን እንደጎበያ
ድንጋይ ጎልታ ልትሄድ! » ለእኔ የሚለው የራስ ወዳድነት ስሜት
ተጠናወተው:: ልቡ የተቃውሞ ኃይል አረገዘ:: ዣን ቫልዣ ይህን እያሰላሰለ ሳለ ሠሪተኛዋ እርሱ ከነበረበት ክፍል ገባች::
«ውጊያ ይካሄዳል ያለሽው የት ሰፈር ነበር? ቦታውን አውቀሽዋል?»
ሠራተኛዋ ተገርማ «እርስዎ ከፈለጉ ምን ገድዶኝ እነግሮታለሁ» ስትል መለሰች::
«ውጊ.ያው ተጧጡፎአል ብለሽ አሁን አልነገርሽኝም እንዴ!» በማለት ቀጠለ::
«አዎን ጌታዬ!›› አለች ሠራተኛዋ ፤ ከዚያ ከማርያም ቤተ ክርስቲያን
ባሻገር ነው:: ››
ዣን ቫልዣ ከነበረበት ውጭ ወጥቶ ደንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡
ጊዜው ጨልሞአል::
ውርጭ ላይ ለምን ያህል ሰዓት ተቀመጠ? እግሩን በመዘርጋትና
በማጣጠፍ ራሱን አዝናና ወይስ ኩርምት ብሎ ነው የቀረው? እንዳጎነበሰ ቀረ ወይስ ቀና አለ? አንድ ነገር ተደግፎ ነው ወይስ እንዲሁ ጉች ብሎ ነው
የተቀመጠው? ራሱ እንኳን ቢሆን ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ሊሰጥ አይችልም።
በአንድ ወቅት የኮቴ ድምፅ ስለሰማ ብቻ ቀና አለ፡፡ አንድ ልጅ ወደ እርሱ ሲመጣ ተመለከተ፡፡ ጋቭሮች መልእክቱን ለማድረስ ከቤቱ ደረሰ። ወደ ላይ እያየ የቤት ቁጥር ሲፈልግ ዣን ቫልዣ አየው:: ሆኖም ከቁጥር አላስገባውም::
«አንተ ልጅ» አለ ዣን ቫልዣ ፧
«ምን ሆነሃል?»
«የሆንኩትማ እርቦኛል» ሲል ጋቭሮች በድፍረት መለሰለት:: ምናምን ይሰጡኛል?» አለ ቀጠለና፡፡
ዣን ቫልዣ ከኪሱ አንድ መቶ ሱስ አወጣና ሰጠው::
ግን ጋቭሮች አደብ የሌለው ተቅበጥባጭ ልጅ እንደመሆኑ መጠን ገንዘቡን እንደ መቀበል ድንጋይ አነሳ፡፡ የሚሰራ የመንገድ መብራት አየ::
«አሁንም የውጭ መብራት ታበራላችሁ እንዴ?» ሲል ጋቭሮች
ጠየቀ፡፡ «በአሁኑ ጊዜ እኮ መብራት ማብራት ጥሩ አይደለም» ካለ በኋላ
ድንጋዩን ወርውሮ መብራቱን ሰበረው፡፡ አካባቢው በድንገት ጨለመ::
ዣን ቫልዣ ወደ ልጁ ተጠጋ::
«ወይ ምስኪን፣ እንዲህ የሚያስደርገው ምናልባት ረሃቡ ይሆናል። ሲል እርስ በራሱ ተነጋገረ፡፡ መቶውን ሱስ አስጨበጠው::
ጋብሮች የምንተ እፍረቱን ገንዘቡን ተቀበለ፡፡
«ሌላ መብራት እንዳልሰብር ነው» አለ እንዳቀረቀረ፡፡
«እንደ ፈለግህ ስበር፧ እኔ ምን አገባኝ» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት።
«ጥሩ ሰው ነዎት!» አለ ጋቭሮች::
አምስቱን ፍራንክ ማለት አንድ መቶ ሱስ ከኪሱ ውስጥ ጨመረ።
ሰውዬውን ስለወደደው በድፍረት ጥያቄ ጠየቀው::
«የዚሁ ሰፈር ሰው ነዎት?»
«ምን ፈለግህ?»
«የቤት ቁጥር 7 የትኛው እንደሆነ ያሳዩኛል?»
«ከዚያ ምን አለህ?»
እዚህ ላይ ልጁ አመነታ:: ሰውዩውን ያስቀየመው መስለው:: ፀጉሩን በጥፍሩ ያክ ጀመር፡፡
«ብቻ» በማለት የያዘውን ደብዳቤ አሳየው::
ዣን ቫልዣ በድንገት አንድ ሀሳብ ስለመጣለት «ስጠብቀው የነበረውን ደብዳቤ አመጣህልኝ» አለው::
«ለእርስዎ?» ሲል ጋቭሮች ጠየቀ፡፡ «እርስዎ ሴት አይደሉ!»
«ደብዳቤው ለወ/ት ኮዜት ነው፤ አይደለም?»
«ኮዜት?» ሲል ጋቭሮች አጉረመረመ:: «አዎን ደብዳቤው የእርሳቸው ነው ፤ ስማቸው ግን ያስቃል፡፡»
«ይሁን ግድ የለም» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «ደብዳቤውን እኔ እሰጣታለሁና
ለእኔ ስጠኝ፡፡»
«እንግዲያውስ ውጊያው ከሚካሄድበት ቦታ እንደመጣ እንዲነግሯት እፈልጋለሁ::»
«ጥሩ» አለ ዣን ቫልዣ::
ጋቭሮች ደብዳቤውን ከሰጠው በኋላ ለዣን ቫልዣ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠው::
«ደብዳቤውን በጥንቃቄ ይያዙት ፤ ከአስተዳደር ነው የመጣው::
እርስዎም ይቸኩላሉ እንዴ? ለመሆኑ ደብዳቤውን የተቀበለው ማነው እላለሁ? ስምዎን ይንገሩኛ ደብዳቤውን ለላኩት እመቤት እንድነግር» ሲል
ኩራት እየተሰማው ተናገረ፡፡
‹‹ጥያቄውን የሚያቀርቡት ቅድስት ፍንዱቄ ናቸው?» ሲል ዣን
ቫልዣ ጠየቀው::
«ቸኩያለሁ፤ ደብዳቤውን ያመጣሁት ከውጊያ ሥፍራ ነው፤ አሁንም ወደዚያው መመለሴ ነው» ብሎ መንገዱን በመቀጠል ሰፈር እንደጠፋበት ወፍ በርሮ ሄደ::
ዣን ቫልዣ ማሪየስ የጻፈውን ደብዳቤ ይዞ ወደ ውስጥ ገባ፡፡ ከክፍሉ ውስጥ ገብቶ በሩን ከዘጋ በኋላ ጥምብ እንዳገኘ አሞራ በመቸኵል ደብዳቤውን
ገለጠው:: የታየሁ እንደሆነ ብሎ በመፍራት ቀና አለና ዙሪያውን ተመለከተ፡፡
ማንም የለም:: ኮዜትና ሠራተኛዋ ተኝተዋል ሲል ግምት ወሰደ::
የሚያደርገው ነገር የሌብነት ስለሆነ ሻማ ለመለኮስ ክብሪት ሲጭር እጁ ተንቀጥቅጦበት ነበር፡፡ አሁን ግን ትንሽ መንፈሱ ስለተረጋጋ ሻማውን አቀጣጠለ፡፡ ከጠረጴዛ ላይ ክርኑን አስደግፎ ደብዳቤውን ማንበብ ጀመረ::
ማሪየስ ለኮዜት ከጻፈው ደብዳቤ ውስጥ የሚከተሉትን ቃላት ብቻ
አጤነ፡፡
«እሞታለሁ፤ ይህን ደብዳቤ ስታነቢ ነፍሴ ከአጠገብሽ ይሆናል፡፡»
👍21👏2❤1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የቤት ውስጥ ጦርነት
ሌሊቱን ሌላ ውጊያ ስላልተካሄደ አድመኞቹ የፈራረሰውን ምሽጋቸውን ለማደስና ለማስፋት ጊዜ አገኙ፡፡ ከቁመቱ ትንሽ ጨመሩለት፡፡ ብረት መከላከያም አበጁ፡፡ ወጥ ቤቱን አጸዳድተው የቁስለኛ ማከሚያ ክፍል
አደረጉት:: የሞቱትን ሰዎች አስከሬን አንስተው ጥግ አስያዙ፡፡ በስርቆሹ በር በኩል ያለውን መግቢያና መውጫ በሚገባ ተጠቀመበት፡፡ ቡና ቤቱ ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ሦስት ሴቶች ጨለማን ተገን በማድረግ በጓሮ በር በኩል ወጥተው በመሄዳቸው አድመኞቹ እፎይታን አገኙ::
ጎህ ሲቀድ ኢንጆልራስ ሁናቴውን ለመቃኘት በስርቆሹ በር በኩል
ወደ ውጭ ወጣ፡፡ አድመኞቹ «እናሸንፋለን» የሚል እምነት ነበራቸው:: ሆኖም ኢንጆልራስ ከተመለሰ በኋላ ሁኔታው በአንድ ጊዜ ተለወጠ፡፡ ኢንጆልራስ በከተማው የነበረው ጦር በሙሉ እነርሱን ሊያጠቃ መውጣቱን
ሕዝቡ ግን ባለፈው ቀን ገንፍሎ ወጣ እንጂ በእለቱ ሁሉም ከቤቱ መከተቱን ሊነግራቸው መሞቻቸው መቃረቡን ጠረጠሩ፡፡ ከመካከላቸው አንዱ «ወንድሞቼ ሕዝቡ ሪፑብሊኩን ሲከዳ እኛ ሕዝቡን አንከዳም፡፡ እኛ አሁን
ማድረግ ያለብን ምሽጋችንን አጠናክረን በአለን ኃይል መዋጋት ነው» ብሎ ተናገረ፡፡
እነዚህ ቃሎች የአድመኞቹን ሞራል ገነቡት፡፡ ይህ ቃል የማን እንደነበር
እስከዛሬ አልታወቀም:: ብቻ ቀቢጸ ተስፋ በሚገኝበት ጊዜ ዘወትር አንዱ ብቅ ብሎ ሁኔታውን እንደሚለውጥ ሁሉ ይህም ከዚህ የተለየ አልነበረም::
ያ «የሕዝብ ወገን ነኝ» የሚለው ሁሉ ተቃውሞውን ካሰማ በኋላ
«እድሜ ለሞት፧ ለዚያች ቅጽበት ሁላችንም እንቆይ!» ሲሉ ሁሉም በአንድነት ጮኹ::
«ለምን ሁላችንም?» ሲል ኢንጂልራስ ጠየቀ፡፡
«ሁላችንም! ሁላችንም!» የሚል ድምፅ አስተጋባ፡፡
«ምሽጉ ጥሩ ነው:: ለመመከት ሰላሳ ሰዎች ይበቃሉ:: ለምን አርባ
ሰዎችን እንሰዋለን» በማለት ኢንጆልራስ ተናገረ::
«ምክንያቱማ ከዚህ ለመሄድ የሚፈልግ ሰው ባለመኖሩ ነዋ!» አሉ ሁሉም በአንድነት::
ኢንጆልራስና ኮምብፌሬ ወደ ምድር ቤት ወርደው አራት የወታደር ልብስ ይዘው መጡ፡፡
«ከመካከላችን ቤተሰብ ማለት የሚጦሯቸው እናት! እህት፣ ሚስት፣ ልጆች ያልዋቸው አይጠፉም፡፡ የዚህ ዓይነት ኃላፊነት ያለባቸው ከዚህ
ይሂዱ» ሲሉ ኢንጆልራስ አሳሰበ፡፡
«እውነት ነው! አሁን እርስዎ ቤተሰብ አለዎት! እርስዎ ቢሄዱ»
በማለት አንዱ ወጣት ከአጠገቡ የነበሩ ጠና ያሉትን ሰው መከራቸው፡፡
«ይልቅስ አንተ ሁለት እህቶችህ በአንተ ላይ አይደለም ያሉት?»
ሁሉም በየፊናው «አንተ ሂድ፣ አንቱ ሂዱ» ሲባባል ጫጫታ ሆነ፡፡
«ወንድሞቼ! የምንዋጋው ለሪፑብሊኩ ነው ! አሁን ጭቅጭቀን ተዉና መሄድ ያለባቸው ይሂዱ» አለ ኢንጆልራስ፡፡
አምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አምስት ሰዎች በኣንድ ድምፅ ተመርጠው እንዲሄዱ ተወሰነ፡፡
«አምስት ናቸው» ሲል ማሪየስ ተናገረ፡፡
የነበረው ዩኒፎርም ግን አራት ነው:: በዚህ ጊዜ ከሰማይ የወረደ
ይመስል አንድ ሌላ ዩኒፎርም ተጣለ፡፡ የአምስተኛው ሰው ሕይወት ዳነ ማለት ነው::
ማሪየስ ልብሱን ማን እንደጣለው ለማየት ቀና ብሎ ሲያይ መሴይ
ፎሽለማንን አየው:: ዣን ቫልዣ ከምሽጉ መግባቱ ነበር፡፡
በጓሮ በኩል ማንም ሳያይ በሚያስገባው መንገድ ነው የገባው:: ያንን መንገድ ቀደም ብሎ ይወቀው ወይም በአጋጣሚ ይድረስበት አይታወቅም፡፡
ከቤቱ ሲወጣ የወታደር ልብስ ለብሶ ስለወጣ ለማለፍ ብዙም አልተቸገረም::
«ይህ ሰው ማነው?» ሲል አንዱ ጠየቀ::
«እሱማ» አለ ኮምብፌሬ የሌሎችን ሕይወት የሚያድን ሰው ነው::
«እኔም አውቀዋለሁ» ሲል ማሪየስ ሀዘን እየተሰማው ተናገረ::
ከዚህ ይበልጥ ሌላ ማረጋገጫ አልተፈለገም:: ኢንጆልራስ ወደ ዣን ቫልዣ ዞረ::
«እንኳን ደህና መጡ፡፡ እንደምንሞት ያውቃሉ?»
ዣን ቫልዣ መልስ ሳይሰጥ ዩኒፎርም የጣለለትን ሰውዬ ያለብስ ጀመር
ምንም እንኳን ጊዜው ረፈድ ቢልም አንድም መስኮት አልተከፈተም።
በሩቁ ግን ሰዎች ከወዲያ ወዲህ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፡፡ ወሳኙ ሰዓት
እንደቀረበ ያስታውቃል፡፡
ኢንጆልራስ ከመጠጥ ቤቱ በራፍ ድንጋይ ቆልሉአል፡፡ እያንዳንዱ
ሰው ለውጊያ እንዲዘጋጅ አስጠነቀቀ፡፡ ብዙም አልጠበቁም፡፡ ከባድ ጦር
ወደነበሩት ሲመጣ ተመለከቱ፡፡ የተኩስ ድምፅ ተሰማ::
«ተኩስ» ሲል ኢንጆልራስ አዘዘ፡፡
ከዚያ በኋላ ምኑ ቅጡ፤ አገር ተቃጠለ፡፡ ሰማዩ ሁሉ በጭስ ተሸፈኑ።ፊት ለፊት የነበረውን ጣልኩ ሲባል ሌላው ከኋላ ብቅ ይላል::
«ቶሎ ቶሎ እያላችሁ ጠብመንጃችሁን አጉርሱ» ሲል ኢንጆልራስ ጮኸ፡
አድመኞቹ ከባድ መሣሪያ መተኰስ ጀመሩ፡፡ ብዙ ስው ተረፈረፈ።ሁሉም በያለበት «ብራቮ፣ ብራቮ» ሲል ጮኸ፡፡ ሁሉም ተተራመሰ፡፡ ጋቭሮች
እየሮጠ ወደፊት መጣ፡፡ ልጁን ሲያዩ ሁሉም ተበራታ::
«ጓዶች በርቱ» ሲል ጋቭሮች ተናገረ:: «በርቱና ተዋጉ፤ ከየአቅጣጫው ብዙ ጦር እየመጣ ነው።»
«ይኸው ነው፤ እስቲ ሞራል ስጥልኝ!» አለ ኢንጆልራስ፡፡ ጦሩ
ሲመጣባቸው «ጭንቅላታችሁን ዝቅ አድርጉ፤ ደግሞም ወደ ግድግዳው ጠጋ በሉ» በማለት ኢንጆልራስ ምክር ለገሠ፡፡ ከባድ መሣሪያ የያዘ ወጣት
መሣሪያውን እየገፋ ሲመጣ ያዩታል:: ኮምብፌሬ ወጣቱን ሲያየው በጣም አዘነ፡፡
«እንዴት ያሳዝናል፧ ምን ዓይነት የጭካኔ ሥራ ነው የሚፈጽሙት።
ምናልባት ንጉሦች ሲጠፉ ጦርነትም ይጠፋ ይሆናል፡፡ ኢንጆልራስ፣ ወጣቱ ላይ ነው እንዴ የምታነጣጥረው ምን ማለትህ ነው? ይህ ወጣት እኮ ገና ለጋ ነው፡፡ ቢበዛ 25 ዓመት ቢሆነው ነው:: ምናልባት የሚጦራቸው አባት ፤ እናት፣ ወንድምና እህት ይኖሩት ይሆናል፡፡ ከዚህም በላይ መልከ ቀና እንደመሆኑ የሚወዳትና የምትወደው ፍቅረኛ ትኖረው ይሆናል።
ደግሞም የእኔ ወይም የአንተ ወንድም ሊሆን ይችላል፡፡»
«እሱማ ነው» ሲል ኢንጆልራስ መለሰለት፡፡
«እንግዲያውማ እርሱን መምታትና መግደል የለብንም።»
«እባክህን ዝም በለኝ፣ ማድረግ ያለብንን እናደርጋለን፡፡
ደም ከመሰለው የኢንጆልራስ ጉንጭ እምባ እንደ ጐርፍ ይወርድ
ጀመር፡፡ ወዲያው የጠመንጃውን ቃታ ሳብ አደረገና ለቀቀው:: ያ ለግላጋ ወጣት ከመሬት ተዘረረ፡፡ አየር ይበላ ይመስል አፉን ከፍቶ ከአንገቱ ቀና አለ፡፡ ይጎትተው ከነበረ ከባድ መሣሪያ ላይ ተደፍቶ ፀጥ እንዳለ ቀረ፡፡ዐከጀርባው ደም ሲፍለቀለቅ ታየ:: የወጣቱ ነፍስ ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ከሥጋው ተለየች::
ውጊያው ቀጠለ፡፡ ስለውጊያው ከዚህ ይበልጥ ዝርዝር ውስጥ ለመግባት ቢፈለግ ሌላ መጽሐፍ ይወጣዋል፡፡ ሆኖም በዚያች ቀውጢ ቀን የነበረው ሁኔታ ስለጦርነቱ ትንሽ መጨመር ያስገድዳል፡፡ የንጉሡ ጦር በሚገባ ተዘጋጅቶ የመጣ ስለነበር የአድመኞቹን ጥይት ለማስጨረስ ፈልጎ ኃይሉን በመበታተን ከተለያየ አቅጣጫ ተኩስ ይከፍታል፡፡ በአንድ ወገን በከባድ መሣሪያ በመጠቀም ምሽጉን አፈራረሰው:: ያንን ለመቋቋም አድመኞቹ
ባላቸው ኃይል በመታኮስ ተከላከሉ፡፡ ይህም በመሆኑ ጊዜያዊ ድልን ተቀዳጁ፡፡
ሁሉም ደስ አላቸው:: ግን የሚያሳዝነው የነበራቸው ጥይት ተገባድዶ ያገኙታል::
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስምንት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የቤት ውስጥ ጦርነት
ሌሊቱን ሌላ ውጊያ ስላልተካሄደ አድመኞቹ የፈራረሰውን ምሽጋቸውን ለማደስና ለማስፋት ጊዜ አገኙ፡፡ ከቁመቱ ትንሽ ጨመሩለት፡፡ ብረት መከላከያም አበጁ፡፡ ወጥ ቤቱን አጸዳድተው የቁስለኛ ማከሚያ ክፍል
አደረጉት:: የሞቱትን ሰዎች አስከሬን አንስተው ጥግ አስያዙ፡፡ በስርቆሹ በር በኩል ያለውን መግቢያና መውጫ በሚገባ ተጠቀመበት፡፡ ቡና ቤቱ ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ሦስት ሴቶች ጨለማን ተገን በማድረግ በጓሮ በር በኩል ወጥተው በመሄዳቸው አድመኞቹ እፎይታን አገኙ::
ጎህ ሲቀድ ኢንጆልራስ ሁናቴውን ለመቃኘት በስርቆሹ በር በኩል
ወደ ውጭ ወጣ፡፡ አድመኞቹ «እናሸንፋለን» የሚል እምነት ነበራቸው:: ሆኖም ኢንጆልራስ ከተመለሰ በኋላ ሁኔታው በአንድ ጊዜ ተለወጠ፡፡ ኢንጆልራስ በከተማው የነበረው ጦር በሙሉ እነርሱን ሊያጠቃ መውጣቱን
ሕዝቡ ግን ባለፈው ቀን ገንፍሎ ወጣ እንጂ በእለቱ ሁሉም ከቤቱ መከተቱን ሊነግራቸው መሞቻቸው መቃረቡን ጠረጠሩ፡፡ ከመካከላቸው አንዱ «ወንድሞቼ ሕዝቡ ሪፑብሊኩን ሲከዳ እኛ ሕዝቡን አንከዳም፡፡ እኛ አሁን
ማድረግ ያለብን ምሽጋችንን አጠናክረን በአለን ኃይል መዋጋት ነው» ብሎ ተናገረ፡፡
እነዚህ ቃሎች የአድመኞቹን ሞራል ገነቡት፡፡ ይህ ቃል የማን እንደነበር
እስከዛሬ አልታወቀም:: ብቻ ቀቢጸ ተስፋ በሚገኝበት ጊዜ ዘወትር አንዱ ብቅ ብሎ ሁኔታውን እንደሚለውጥ ሁሉ ይህም ከዚህ የተለየ አልነበረም::
ያ «የሕዝብ ወገን ነኝ» የሚለው ሁሉ ተቃውሞውን ካሰማ በኋላ
«እድሜ ለሞት፧ ለዚያች ቅጽበት ሁላችንም እንቆይ!» ሲሉ ሁሉም በአንድነት ጮኹ::
«ለምን ሁላችንም?» ሲል ኢንጂልራስ ጠየቀ፡፡
«ሁላችንም! ሁላችንም!» የሚል ድምፅ አስተጋባ፡፡
«ምሽጉ ጥሩ ነው:: ለመመከት ሰላሳ ሰዎች ይበቃሉ:: ለምን አርባ
ሰዎችን እንሰዋለን» በማለት ኢንጆልራስ ተናገረ::
«ምክንያቱማ ከዚህ ለመሄድ የሚፈልግ ሰው ባለመኖሩ ነዋ!» አሉ ሁሉም በአንድነት::
ኢንጆልራስና ኮምብፌሬ ወደ ምድር ቤት ወርደው አራት የወታደር ልብስ ይዘው መጡ፡፡
«ከመካከላችን ቤተሰብ ማለት የሚጦሯቸው እናት! እህት፣ ሚስት፣ ልጆች ያልዋቸው አይጠፉም፡፡ የዚህ ዓይነት ኃላፊነት ያለባቸው ከዚህ
ይሂዱ» ሲሉ ኢንጆልራስ አሳሰበ፡፡
«እውነት ነው! አሁን እርስዎ ቤተሰብ አለዎት! እርስዎ ቢሄዱ»
በማለት አንዱ ወጣት ከአጠገቡ የነበሩ ጠና ያሉትን ሰው መከራቸው፡፡
«ይልቅስ አንተ ሁለት እህቶችህ በአንተ ላይ አይደለም ያሉት?»
ሁሉም በየፊናው «አንተ ሂድ፣ አንቱ ሂዱ» ሲባባል ጫጫታ ሆነ፡፡
«ወንድሞቼ! የምንዋጋው ለሪፑብሊኩ ነው ! አሁን ጭቅጭቀን ተዉና መሄድ ያለባቸው ይሂዱ» አለ ኢንጆልራስ፡፡
አምስት ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አምስት ሰዎች በኣንድ ድምፅ ተመርጠው እንዲሄዱ ተወሰነ፡፡
«አምስት ናቸው» ሲል ማሪየስ ተናገረ፡፡
የነበረው ዩኒፎርም ግን አራት ነው:: በዚህ ጊዜ ከሰማይ የወረደ
ይመስል አንድ ሌላ ዩኒፎርም ተጣለ፡፡ የአምስተኛው ሰው ሕይወት ዳነ ማለት ነው::
ማሪየስ ልብሱን ማን እንደጣለው ለማየት ቀና ብሎ ሲያይ መሴይ
ፎሽለማንን አየው:: ዣን ቫልዣ ከምሽጉ መግባቱ ነበር፡፡
በጓሮ በኩል ማንም ሳያይ በሚያስገባው መንገድ ነው የገባው:: ያንን መንገድ ቀደም ብሎ ይወቀው ወይም በአጋጣሚ ይድረስበት አይታወቅም፡፡
ከቤቱ ሲወጣ የወታደር ልብስ ለብሶ ስለወጣ ለማለፍ ብዙም አልተቸገረም::
«ይህ ሰው ማነው?» ሲል አንዱ ጠየቀ::
«እሱማ» አለ ኮምብፌሬ የሌሎችን ሕይወት የሚያድን ሰው ነው::
«እኔም አውቀዋለሁ» ሲል ማሪየስ ሀዘን እየተሰማው ተናገረ::
ከዚህ ይበልጥ ሌላ ማረጋገጫ አልተፈለገም:: ኢንጆልራስ ወደ ዣን ቫልዣ ዞረ::
«እንኳን ደህና መጡ፡፡ እንደምንሞት ያውቃሉ?»
ዣን ቫልዣ መልስ ሳይሰጥ ዩኒፎርም የጣለለትን ሰውዬ ያለብስ ጀመር
ምንም እንኳን ጊዜው ረፈድ ቢልም አንድም መስኮት አልተከፈተም።
በሩቁ ግን ሰዎች ከወዲያ ወዲህ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፡፡ ወሳኙ ሰዓት
እንደቀረበ ያስታውቃል፡፡
ኢንጆልራስ ከመጠጥ ቤቱ በራፍ ድንጋይ ቆልሉአል፡፡ እያንዳንዱ
ሰው ለውጊያ እንዲዘጋጅ አስጠነቀቀ፡፡ ብዙም አልጠበቁም፡፡ ከባድ ጦር
ወደነበሩት ሲመጣ ተመለከቱ፡፡ የተኩስ ድምፅ ተሰማ::
«ተኩስ» ሲል ኢንጆልራስ አዘዘ፡፡
ከዚያ በኋላ ምኑ ቅጡ፤ አገር ተቃጠለ፡፡ ሰማዩ ሁሉ በጭስ ተሸፈኑ።ፊት ለፊት የነበረውን ጣልኩ ሲባል ሌላው ከኋላ ብቅ ይላል::
«ቶሎ ቶሎ እያላችሁ ጠብመንጃችሁን አጉርሱ» ሲል ኢንጆልራስ ጮኸ፡
አድመኞቹ ከባድ መሣሪያ መተኰስ ጀመሩ፡፡ ብዙ ስው ተረፈረፈ።ሁሉም በያለበት «ብራቮ፣ ብራቮ» ሲል ጮኸ፡፡ ሁሉም ተተራመሰ፡፡ ጋቭሮች
እየሮጠ ወደፊት መጣ፡፡ ልጁን ሲያዩ ሁሉም ተበራታ::
«ጓዶች በርቱ» ሲል ጋቭሮች ተናገረ:: «በርቱና ተዋጉ፤ ከየአቅጣጫው ብዙ ጦር እየመጣ ነው።»
«ይኸው ነው፤ እስቲ ሞራል ስጥልኝ!» አለ ኢንጆልራስ፡፡ ጦሩ
ሲመጣባቸው «ጭንቅላታችሁን ዝቅ አድርጉ፤ ደግሞም ወደ ግድግዳው ጠጋ በሉ» በማለት ኢንጆልራስ ምክር ለገሠ፡፡ ከባድ መሣሪያ የያዘ ወጣት
መሣሪያውን እየገፋ ሲመጣ ያዩታል:: ኮምብፌሬ ወጣቱን ሲያየው በጣም አዘነ፡፡
«እንዴት ያሳዝናል፧ ምን ዓይነት የጭካኔ ሥራ ነው የሚፈጽሙት።
ምናልባት ንጉሦች ሲጠፉ ጦርነትም ይጠፋ ይሆናል፡፡ ኢንጆልራስ፣ ወጣቱ ላይ ነው እንዴ የምታነጣጥረው ምን ማለትህ ነው? ይህ ወጣት እኮ ገና ለጋ ነው፡፡ ቢበዛ 25 ዓመት ቢሆነው ነው:: ምናልባት የሚጦራቸው አባት ፤ እናት፣ ወንድምና እህት ይኖሩት ይሆናል፡፡ ከዚህም በላይ መልከ ቀና እንደመሆኑ የሚወዳትና የምትወደው ፍቅረኛ ትኖረው ይሆናል።
ደግሞም የእኔ ወይም የአንተ ወንድም ሊሆን ይችላል፡፡»
«እሱማ ነው» ሲል ኢንጆልራስ መለሰለት፡፡
«እንግዲያውማ እርሱን መምታትና መግደል የለብንም።»
«እባክህን ዝም በለኝ፣ ማድረግ ያለብንን እናደርጋለን፡፡
ደም ከመሰለው የኢንጆልራስ ጉንጭ እምባ እንደ ጐርፍ ይወርድ
ጀመር፡፡ ወዲያው የጠመንጃውን ቃታ ሳብ አደረገና ለቀቀው:: ያ ለግላጋ ወጣት ከመሬት ተዘረረ፡፡ አየር ይበላ ይመስል አፉን ከፍቶ ከአንገቱ ቀና አለ፡፡ ይጎትተው ከነበረ ከባድ መሣሪያ ላይ ተደፍቶ ፀጥ እንዳለ ቀረ፡፡ዐከጀርባው ደም ሲፍለቀለቅ ታየ:: የወጣቱ ነፍስ ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ከሥጋው ተለየች::
ውጊያው ቀጠለ፡፡ ስለውጊያው ከዚህ ይበልጥ ዝርዝር ውስጥ ለመግባት ቢፈለግ ሌላ መጽሐፍ ይወጣዋል፡፡ ሆኖም በዚያች ቀውጢ ቀን የነበረው ሁኔታ ስለጦርነቱ ትንሽ መጨመር ያስገድዳል፡፡ የንጉሡ ጦር በሚገባ ተዘጋጅቶ የመጣ ስለነበር የአድመኞቹን ጥይት ለማስጨረስ ፈልጎ ኃይሉን በመበታተን ከተለያየ አቅጣጫ ተኩስ ይከፍታል፡፡ በአንድ ወገን በከባድ መሣሪያ በመጠቀም ምሽጉን አፈራረሰው:: ያንን ለመቋቋም አድመኞቹ
ባላቸው ኃይል በመታኮስ ተከላከሉ፡፡ ይህም በመሆኑ ጊዜያዊ ድልን ተቀዳጁ፡፡
ሁሉም ደስ አላቸው:: ግን የሚያሳዝነው የነበራቸው ጥይት ተገባድዶ ያገኙታል::
👍16
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....የሞቱት ሰዎች አስከሬን
ከመውጫው ላይ ተቆልሎ ስለነበር በችግር ነው ያለፉት:: የሰው ሬሣ እንደ ድንጋይ ተቆልሎ ማየቱም በጣም አሰቃቂ ነበር፡፡
ቁና ዣቬር በረጋ መንፈስ «ይህችን ልጅ አውቃት ነበር» ሲል ድምፁን ዝቅ አድርጎ የኢፖኒን የተገላለጠ ጡትና ገላ እያየ ይናገራል፡፡ ከዚያም ወደ
ዣን ቫልዣ ዞር አለ፡፡"
ዣን ቫልዣ ቃል ሳይናገር ዝም ብሎ በማፍጠጥ አየው:: ደግሞ
መናገርም አያስፈልግም ነበር፡፡ አስተያየቱ ብቻ ዣቬር እኔው ነኝ!» ለማለቱ ግልጽ ነበር፡፡
ዣቬር ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አሁን ልትበቀለኝ ትችላለህ::»
ዣን ቫልዣ ሽጉጡን ከኪሱ ከከተተ በኋላ ሰንጢውን አወጣ፡፡ ሰንጢውን ዘረጋው፡፡
«ወይ ጉድ!» አለ ዣቬር፡፡ «ልክ ነህ፣ እሱ ይሻልሃል»
«ፊትህን አዙር» ሲል ዣቬርን አዘዘው:: ዣቬርም ፊቱን ወደ
ግድግዳው አዞረ:: ከዚያም ዣን ቫልዣ ጠላቱ የፍጥኝ የታሠረበትን ገመድ ይቆርጥ ጀመር፡፡ እጁንና እግሩን አላቀቀለት:: እግሮቹ የታሠሩባቸውን ገመድ ቆርጦ እንደጨረሰ እዚያው ከመሬት ሆኖ ዣቬርን ቀና ብሎ አያየ
«መሄድ ትችላለህ» አለው::
ዣቬር ግራ ተጋብቶ አፉን እንደከፈተ ቀረ:: ዣን ቫልዣ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«እኔ ግን ከዚሁ ማለት ከምሽጉ ውስጥ እቆያለሁ፡፡ ምናልባት በአጋጣሚ በሕይወት ከወጣሁ አድራሻዬን ልስጥህ» ብሎ የቤቱን አድራሻ ሰጠው።ዣቬር በመገረም እያየውና ከንፈሩን በግድ አላቅቆ «ራስህን ጠብቅ» ሲል መከረው::
«ለማንኛውም ሂድ ብያለሁ፤ ቶሎ ብለህ ከዚህ ጥፋ» ሲል ዣን
ቫልዣ በተራው መከረው::
ዣቬር አድራሻውን ለማረጋገጥ «ሆም አርሚ ጐዳና የቤት ቁጥር
ሰባት ነው ያልከኝ?» ሲል ጠየቀው::
«በደምብ ይዘኸዋል» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት::
ዣቬር ልብሱን አስተካክሎና በአንድ እጁ ጉንጩን ይዞ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያው እንደቆመ በዓይኑ ተከተለው:: ዣቬር ጥቂት
ከተጓዘ በኋላ ወደ ኋላ መለስ ብሎ «አናደድከኝ፣ ለምን አልገደልከኝም ነበር»ሲል ተናገረው:: «ሂድ ብያለሁ፤ ሂድ» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት።
ዣቬር በዝግታ እየተራመደ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ኩርባ ላይ ሲደርስ ወደ ግራ ታጠፈ::ዣቬር ከዓይኑ ሲሰወር ዣን ቫልዣ ሁለት ጊዜ ወደ ሰማይ ተኩሰ፡፡ ከዚያም ወደ ምሽጉ ተመልሶ «እርምጃው ተወስዷል» ሲል ሪፖርቱን አቀረበ።
«አጥቃ» የሚለው የከበሮ ምልክት እንደገና በኃይል ተመታ፡፡ ማጥቃቱ እርምጃ ከማዕበል የከፋ ነበር፡፡ እግረኛው ጦር ጠመንጃን ወድሮ በቀጥታ ወደ ምሽጉ ገሠገሠ፡፡ መለከቱና ከበሮው ተንጣጣ፡፡ የእግረኛው እርምጃ መሬቱን አነቃነቀው::
ከምሽጉ ውስጥ በሕይወት የቀሩት አድመኞች ጠመንጃቸውን
አንጣጡት:: ኢንጆልራስ በአንድ ፊት ማሪየስ በሌላ በኩል አጋሮቻቸውን ለማነቃቃት ይጮሃሉ፡፡ ጦሩ እየቀረባቸው መጣ፡፡ ከአጠገባቸው የደረሰው
እየተንገዳገደ ከእግራቸው ስር ይወድቃል:: ኃይለኛ የመከላከያ ምሽግን ተገን አድርጎ በቀዳዳ የሚዋጋን ጦር ቶሎ ለመጣል ያዳግታል። ሆኖም ! የነበረው
ምንም እንኳን የምሽጉ አቀማመጥ ቢረዳቸውም በመጨረሻ ለመቋቋም አልቻሉም።
እህል ከቀመሱና የእንቅልፍ ዓይን ካዩ ሃያ አራት ሰዓታት ኣልፈዋል።
ቁጥራቸው አንድ ስልሣ ይሆናል:: የነበራቸው ጥይት እየተሟጠጠ ነው።ከመካከላቸው ያልቆሰለ ቢኖር በጣም ጥቂት ነው፡፡ የመንግሥት ጦር ከምሽጉ ለመግባት አሥር ጊዜ ያህል ሞክሮአል፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉ ደረት
ለደረት በጠብመንጃና በጎራዴ በመከላከል በሙሉ ልብ ተዋጉ፡፡ በዚህ ውጊያ እነኩርፌይራክ፣ ቦሌይና ሌሎችም ሲሞቱ ኮምብፌሬ በሳንጃ ደረቱ ላይ
ከሦስት ቦታ ተወግቷል፡፡ እሱም ቢሆን ከተወጋ በኋላ ብዙ አልቆየም፧ ሕይወቱ አለፈች፡፡ ማሪየስ እስከመጨረሻው ቢዋጋም ቆስሉ ስለነበር እየደከመ
ሄደ፡፡ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር ያልተነካው::
በየአቅጣጫው ጥግ ይዞ ይዋጋ የነበረው ሰው ቀስ በቀስ አንዱ
ከሌላው ቀጥሎ ስለተመታና ስለወደቀ ወደ ምሽጉ የሚያስገባ ቀዳዳ እየሰፋ ሄደ፡፡ የመንግሥት ጦርም ከምሽጉ መሃል ለመግባት ቻለ፡፡ ሰው ሲያልቅ የምሽጉ የውጭ ግምብም በመሣሪያ ኃይል ተናደ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር በሕይወት የቆዩት እጅግ ጥቂት አድመኞች የመጨረሻውን መንፈራገጥ ያሳዩት።በዚህች የመጨረሻ ደቂቃ ነው የሰው ልጅ የመኖር ፍላጎቱ የሚያይልበትና
የእንስሳ ባሕርዩ የሚጎላው:: ያቺን ሰዓት ለማለፍ የማያስበው ዘዴና
የማያልመው መላ አይኖርም፡፡ ወደ ፎቅ የሚሮጠውን የተዘጋ በር ለመክፈት የሚታገለው፤ ተከፍቶ የነበረውን በር ላመቀርቀር የሚሽቀዳደመው ሲታይ
በጣም አሳዛኝ ትርዒት ነበር::
በዚያች ቀውጢ ሰዓት በድንጋጤ መንፈሱ ተረብሾ ወደ ስርቆቱ በር
የሚወስደውን መንገድ በጉልህ ያስታወሰ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር፡፡ በአንድ እጁ ጠመንጃውን በሌላው ጎራዴ ይዞ ከፊት ለፊት የሚመጣውን ጦር እየተከላከለ በሕይወት የቀሩትን ሰዎች ወደ ውስጥ እንዳስገባ ወታደሮች
ደርሰው የብረቱን በር ለመግፋት ይታገላሉ:: አድመኞቹ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው በሩን ሲገፉ አንድ ወታደር ጣቱ በበሩ በመቀርጠፉ ይጮሃል፡፡
ማሪየስ በመመታቱ በበሩ አላለፈም:: እንዲያውም ከነአካቴው ሕሊናውን ስቶ ይወድቃል፡፡ ልክ ሲወድቅ አንድ ሰው መጥቶ ሲይዘው
ይታወቀው እንጂ ከዚያ በኋላ የሆነውን አያውቅም:: ከዚያ ጥቂት ቀደም ብሎ እንደ ተመታ ኮዜት ትዝ ብላው «ስለቆሰልኩ እማረካለሁ፤ ከዚያም
በጥይት ተደብድቤ እሞታለሁ» ሲል ያስባል፡፡ ልክ ኮዜት አጠገቡ እንዳለች ቆጥሮ ነበር ታሪኩን የሚነግራት::
እነ ኢንጂልራስ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው ከአንደኛ ፎቅ ላይ የነበረውን ክፍል በር በጥይት አጋዩት:: በዚያች ሰዓት የነበረው ጩኸት ! የነበረው ዋይታና የስቃይ እንጉርጉር በቃላት ለመግለጽ እጅግ በጣም
ስለሚያዳግት እንዲያው ዝም ይሻላል፡፡
በመጨረሻ በሩ ተበርግዶ ሲከፈት በሕይወት የቆየው ኢንጂልራስ
ብቻ ነበር፡፡ ኢንጆልራስ ጥይት አልቀበት ሰውነቱ በደም ተበክሎና ልብሱ ተቦጫጭቆ ጥግ ይዞ ቆሞአል፡፡ ጠመንጃውን ግን በእጁ እንደያዘ ነው።አንድ ሰው ገና ሲያየው በኃይል እየጮኸ ይናገራል::
«መሪው እሱ ነው፡፡ ያንን መልከ መልካም ወጣት የገደለ እርሱ
ነው:: እዚህቹ ከቆመበት በሉት::»
«ግደሉኝ» አለ ኢንጆልራስ ረጋ ብሎ ደረቱን እየገለበጠ፡፡
አሥራ ሁለት ወታደሮች ኢንጆልራስ ላይ ለመተኰስ ጥግ ይዘው
ጠመንጃቸውን አቀኑ።
የሃምሣ አለቃ «ለመተኩስ ተዘጋጁ» ሲል ትእዛዝ ሰጠ::
የሃምሳ አለቃው ጩኸት ግራናትዬን ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ግራናትዬ ከሰካራሞቹ አንዱ ነው:: ከመጠጥ ቤቱ ተኝቶ እንቅልፍ የወሰደው ከአንድ ቀን በፊት ነበር::
እንደሚታወቀው ሰካራም አንዴ እንቅልፍ ከወሰደው እንቅልፉን
ካልጨረሰ በቀር ምንም ዓይነት ድምፅ አይቀሰቅሰውም፡፡ ከእንቅልፉ እንደነቃ በእንቅልፍ ልቡ «ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር፤ እኔም የዚያው አባል ነኝ
በማለት ጮክ ብሉ ሲናገር ወታደሮቹ ደንግጠው ወደ ግራናትዬ ፊታቸውን
አዞሩ፡፡
ሰካራሙ ከተኛበት ብድግ ይላል:: ሁለም አፍጥጦ ያየዋል፡፡
የሚያናግረው ግን የለም::
«ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር» ይላል በድጋሚ፡፡ በቀጥታ ወደ ኢንጆልራስ ሄዶ ከአጠገቡ ቆመ::
«በአንድ ጥይት ሁለት ሰው» ይላል:: ከዚያም ወደ ኢንጆልራስ ዞር ብሎ ረጋ ባለ መንፈስ «አብሬህ ብሞት ትፈቅድልኛህ?» ሲል ጠየቀው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....የሞቱት ሰዎች አስከሬን
ከመውጫው ላይ ተቆልሎ ስለነበር በችግር ነው ያለፉት:: የሰው ሬሣ እንደ ድንጋይ ተቆልሎ ማየቱም በጣም አሰቃቂ ነበር፡፡
ቁና ዣቬር በረጋ መንፈስ «ይህችን ልጅ አውቃት ነበር» ሲል ድምፁን ዝቅ አድርጎ የኢፖኒን የተገላለጠ ጡትና ገላ እያየ ይናገራል፡፡ ከዚያም ወደ
ዣን ቫልዣ ዞር አለ፡፡"
ዣን ቫልዣ ቃል ሳይናገር ዝም ብሎ በማፍጠጥ አየው:: ደግሞ
መናገርም አያስፈልግም ነበር፡፡ አስተያየቱ ብቻ ዣቬር እኔው ነኝ!» ለማለቱ ግልጽ ነበር፡፡
ዣቬር ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«አሁን ልትበቀለኝ ትችላለህ::»
ዣን ቫልዣ ሽጉጡን ከኪሱ ከከተተ በኋላ ሰንጢውን አወጣ፡፡ ሰንጢውን ዘረጋው፡፡
«ወይ ጉድ!» አለ ዣቬር፡፡ «ልክ ነህ፣ እሱ ይሻልሃል»
«ፊትህን አዙር» ሲል ዣቬርን አዘዘው:: ዣቬርም ፊቱን ወደ
ግድግዳው አዞረ:: ከዚያም ዣን ቫልዣ ጠላቱ የፍጥኝ የታሠረበትን ገመድ ይቆርጥ ጀመር፡፡ እጁንና እግሩን አላቀቀለት:: እግሮቹ የታሠሩባቸውን ገመድ ቆርጦ እንደጨረሰ እዚያው ከመሬት ሆኖ ዣቬርን ቀና ብሎ አያየ
«መሄድ ትችላለህ» አለው::
ዣቬር ግራ ተጋብቶ አፉን እንደከፈተ ቀረ:: ዣን ቫልዣ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«እኔ ግን ከዚሁ ማለት ከምሽጉ ውስጥ እቆያለሁ፡፡ ምናልባት በአጋጣሚ በሕይወት ከወጣሁ አድራሻዬን ልስጥህ» ብሎ የቤቱን አድራሻ ሰጠው።ዣቬር በመገረም እያየውና ከንፈሩን በግድ አላቅቆ «ራስህን ጠብቅ» ሲል መከረው::
«ለማንኛውም ሂድ ብያለሁ፤ ቶሎ ብለህ ከዚህ ጥፋ» ሲል ዣን
ቫልዣ በተራው መከረው::
ዣቬር አድራሻውን ለማረጋገጥ «ሆም አርሚ ጐዳና የቤት ቁጥር
ሰባት ነው ያልከኝ?» ሲል ጠየቀው::
«በደምብ ይዘኸዋል» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት::
ዣቬር ልብሱን አስተካክሎና በአንድ እጁ ጉንጩን ይዞ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያው እንደቆመ በዓይኑ ተከተለው:: ዣቬር ጥቂት
ከተጓዘ በኋላ ወደ ኋላ መለስ ብሎ «አናደድከኝ፣ ለምን አልገደልከኝም ነበር»ሲል ተናገረው:: «ሂድ ብያለሁ፤ ሂድ» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰለት።
ዣቬር በዝግታ እየተራመደ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ኩርባ ላይ ሲደርስ ወደ ግራ ታጠፈ::ዣቬር ከዓይኑ ሲሰወር ዣን ቫልዣ ሁለት ጊዜ ወደ ሰማይ ተኩሰ፡፡ ከዚያም ወደ ምሽጉ ተመልሶ «እርምጃው ተወስዷል» ሲል ሪፖርቱን አቀረበ።
«አጥቃ» የሚለው የከበሮ ምልክት እንደገና በኃይል ተመታ፡፡ ማጥቃቱ እርምጃ ከማዕበል የከፋ ነበር፡፡ እግረኛው ጦር ጠመንጃን ወድሮ በቀጥታ ወደ ምሽጉ ገሠገሠ፡፡ መለከቱና ከበሮው ተንጣጣ፡፡ የእግረኛው እርምጃ መሬቱን አነቃነቀው::
ከምሽጉ ውስጥ በሕይወት የቀሩት አድመኞች ጠመንጃቸውን
አንጣጡት:: ኢንጆልራስ በአንድ ፊት ማሪየስ በሌላ በኩል አጋሮቻቸውን ለማነቃቃት ይጮሃሉ፡፡ ጦሩ እየቀረባቸው መጣ፡፡ ከአጠገባቸው የደረሰው
እየተንገዳገደ ከእግራቸው ስር ይወድቃል:: ኃይለኛ የመከላከያ ምሽግን ተገን አድርጎ በቀዳዳ የሚዋጋን ጦር ቶሎ ለመጣል ያዳግታል። ሆኖም ! የነበረው
ምንም እንኳን የምሽጉ አቀማመጥ ቢረዳቸውም በመጨረሻ ለመቋቋም አልቻሉም።
እህል ከቀመሱና የእንቅልፍ ዓይን ካዩ ሃያ አራት ሰዓታት ኣልፈዋል።
ቁጥራቸው አንድ ስልሣ ይሆናል:: የነበራቸው ጥይት እየተሟጠጠ ነው።ከመካከላቸው ያልቆሰለ ቢኖር በጣም ጥቂት ነው፡፡ የመንግሥት ጦር ከምሽጉ ለመግባት አሥር ጊዜ ያህል ሞክሮአል፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉ ደረት
ለደረት በጠብመንጃና በጎራዴ በመከላከል በሙሉ ልብ ተዋጉ፡፡ በዚህ ውጊያ እነኩርፌይራክ፣ ቦሌይና ሌሎችም ሲሞቱ ኮምብፌሬ በሳንጃ ደረቱ ላይ
ከሦስት ቦታ ተወግቷል፡፡ እሱም ቢሆን ከተወጋ በኋላ ብዙ አልቆየም፧ ሕይወቱ አለፈች፡፡ ማሪየስ እስከመጨረሻው ቢዋጋም ቆስሉ ስለነበር እየደከመ
ሄደ፡፡ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር ያልተነካው::
በየአቅጣጫው ጥግ ይዞ ይዋጋ የነበረው ሰው ቀስ በቀስ አንዱ
ከሌላው ቀጥሎ ስለተመታና ስለወደቀ ወደ ምሽጉ የሚያስገባ ቀዳዳ እየሰፋ ሄደ፡፡ የመንግሥት ጦርም ከምሽጉ መሃል ለመግባት ቻለ፡፡ ሰው ሲያልቅ የምሽጉ የውጭ ግምብም በመሣሪያ ኃይል ተናደ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር በሕይወት የቆዩት እጅግ ጥቂት አድመኞች የመጨረሻውን መንፈራገጥ ያሳዩት።በዚህች የመጨረሻ ደቂቃ ነው የሰው ልጅ የመኖር ፍላጎቱ የሚያይልበትና
የእንስሳ ባሕርዩ የሚጎላው:: ያቺን ሰዓት ለማለፍ የማያስበው ዘዴና
የማያልመው መላ አይኖርም፡፡ ወደ ፎቅ የሚሮጠውን የተዘጋ በር ለመክፈት የሚታገለው፤ ተከፍቶ የነበረውን በር ላመቀርቀር የሚሽቀዳደመው ሲታይ
በጣም አሳዛኝ ትርዒት ነበር::
በዚያች ቀውጢ ሰዓት በድንጋጤ መንፈሱ ተረብሾ ወደ ስርቆቱ በር
የሚወስደውን መንገድ በጉልህ ያስታወሰ ኢንጆልራስ ብቻ ነበር፡፡ በአንድ እጁ ጠመንጃውን በሌላው ጎራዴ ይዞ ከፊት ለፊት የሚመጣውን ጦር እየተከላከለ በሕይወት የቀሩትን ሰዎች ወደ ውስጥ እንዳስገባ ወታደሮች
ደርሰው የብረቱን በር ለመግፋት ይታገላሉ:: አድመኞቹ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው በሩን ሲገፉ አንድ ወታደር ጣቱ በበሩ በመቀርጠፉ ይጮሃል፡፡
ማሪየስ በመመታቱ በበሩ አላለፈም:: እንዲያውም ከነአካቴው ሕሊናውን ስቶ ይወድቃል፡፡ ልክ ሲወድቅ አንድ ሰው መጥቶ ሲይዘው
ይታወቀው እንጂ ከዚያ በኋላ የሆነውን አያውቅም:: ከዚያ ጥቂት ቀደም ብሎ እንደ ተመታ ኮዜት ትዝ ብላው «ስለቆሰልኩ እማረካለሁ፤ ከዚያም
በጥይት ተደብድቤ እሞታለሁ» ሲል ያስባል፡፡ ልክ ኮዜት አጠገቡ እንዳለች ቆጥሮ ነበር ታሪኩን የሚነግራት::
እነ ኢንጂልራስ ከውስጥ ወታደሮች ከውጭ ሆነው ከአንደኛ ፎቅ ላይ የነበረውን ክፍል በር በጥይት አጋዩት:: በዚያች ሰዓት የነበረው ጩኸት ! የነበረው ዋይታና የስቃይ እንጉርጉር በቃላት ለመግለጽ እጅግ በጣም
ስለሚያዳግት እንዲያው ዝም ይሻላል፡፡
በመጨረሻ በሩ ተበርግዶ ሲከፈት በሕይወት የቆየው ኢንጂልራስ
ብቻ ነበር፡፡ ኢንጆልራስ ጥይት አልቀበት ሰውነቱ በደም ተበክሎና ልብሱ ተቦጫጭቆ ጥግ ይዞ ቆሞአል፡፡ ጠመንጃውን ግን በእጁ እንደያዘ ነው።አንድ ሰው ገና ሲያየው በኃይል እየጮኸ ይናገራል::
«መሪው እሱ ነው፡፡ ያንን መልከ መልካም ወጣት የገደለ እርሱ
ነው:: እዚህቹ ከቆመበት በሉት::»
«ግደሉኝ» አለ ኢንጆልራስ ረጋ ብሎ ደረቱን እየገለበጠ፡፡
አሥራ ሁለት ወታደሮች ኢንጆልራስ ላይ ለመተኰስ ጥግ ይዘው
ጠመንጃቸውን አቀኑ።
የሃምሣ አለቃ «ለመተኩስ ተዘጋጁ» ሲል ትእዛዝ ሰጠ::
የሃምሳ አለቃው ጩኸት ግራናትዬን ከእንቅልፉ ቀሰቀሰው:: ግራናትዬ ከሰካራሞቹ አንዱ ነው:: ከመጠጥ ቤቱ ተኝቶ እንቅልፍ የወሰደው ከአንድ ቀን በፊት ነበር::
እንደሚታወቀው ሰካራም አንዴ እንቅልፍ ከወሰደው እንቅልፉን
ካልጨረሰ በቀር ምንም ዓይነት ድምፅ አይቀሰቅሰውም፡፡ ከእንቅልፉ እንደነቃ በእንቅልፍ ልቡ «ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር፤ እኔም የዚያው አባል ነኝ
በማለት ጮክ ብሉ ሲናገር ወታደሮቹ ደንግጠው ወደ ግራናትዬ ፊታቸውን
አዞሩ፡፡
ሰካራሙ ከተኛበት ብድግ ይላል:: ሁለም አፍጥጦ ያየዋል፡፡
የሚያናግረው ግን የለም::
«ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር» ይላል በድጋሚ፡፡ በቀጥታ ወደ ኢንጆልራስ ሄዶ ከአጠገቡ ቆመ::
«በአንድ ጥይት ሁለት ሰው» ይላል:: ከዚያም ወደ ኢንጆልራስ ዞር ብሎ ረጋ ባለ መንፈስ «አብሬህ ብሞት ትፈቅድልኛህ?» ሲል ጠየቀው።
👍18❤2
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ከብርሃን ወደ ጨለማ
ዣን ቫልዣ ከፓሪስ ከተማ ባህር ውስጥ ነው የገባው:: ከባህር ውስጥ የገባ ዋናተኛ ሊጠፋ እንደሚችል ሁሉ እርሱም ሊጠፋ ይችላል፡፡ ከብርሃን ወደ ጨለማ ነው የተጓዘው:: በእጁ ፋኖስ ወይም ሌላ መብራት የለም፡፡
ሆኖም ከሞት አፋፍ ደርሶ የነበረው ዣን ቫልዣ ማንም ሊደርስበት ከማይችል
ሥፍራ ነው የሄደው:: ከመሃል ከተማ ወጥቶ ሰው ከማይደርስበት ገጠር ነው የገባው ለማለት ይቻላል፡፡ ከጫጫታና ከሁካታ ወደ ፀጥታ ነው የተሸጋገረው:: ከሞት ወደ ደኅንነት ነው የተዛወረው:: እንዲህ ያለው ነው መልካም አጋጣሚ የሚባለው:: ተፈጥሮ ሆን ብላ ዣን ቫልዣን ለማዳን ያዘጋጀችው ይመስላል፡፡
ማሪየስ ነቅነቅ እንኳን አላለም፡፡ ይሙት ወይም በሕይወት ይኑር
አይታወቅም፡፡ መሬት ሊወድቅ ሲል ዣን ቫልዣ ካነሳው ጀምሮ ሕሊናውን እንደሳተ ነው::
ዣን ቫልዣ ያለበትን ሥፍራ ለማወቅ መጀመሪያ ቀኝ እጁን፤ በኋላም ግራ እጁን ወደ ጐን ዘረጋ፡፡ በሁለቱም በኩል ግድግዳ ነካ፡፡ የቆመበትን ቦታ ጎን ስፋት በዚህ አረጋገጠ፡፡ ቀስ እያለ ወደፊት ተራመደ፡፡ መሬቱ ይርጠብ
እንጂ የተነጠፈ ድንጋይ በመሆኑ ቀዳዳ ነገር እንደሌለው ተረዳ፡፡ ስለዚህ የየቆሻሻ መውረጃው አሠራር እንዴት እንደሆነ ስለሚያውቅ ምን ውስጥ
እንደገባ ያውቃል፡፡
አሁን ካለበት አካባቢ እጅግ በጣም አነስተኛ የሆነ ብርሃን በዚያች በብረት ክዳን በኩል ይገባ ስለነበር እንደ ውጋገን ያለ ነገር ይታያል፡፡ስለቦታው ለማወቅ ፈልጎ ጥቂት ወደፊት በተራመደ ጊዜ ግን ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ ሆነበት:: ማሪየስን እንደገና ተሸክሞ ሃምሳ እርምጃ ያህል ከተራመደ
በኋላ ቆም አለ፡፡ ከቆሻሻ መውረጃ መንታ መንገድ ላይ ደረሰ፡፡ እንዲያውም ከግድግዳ ጋር ሊጋጭ ሲል ለትንሽ ነው የዳነው:: የቀኙን ወይስ የግራውን
መንገድ ይከተል? በዚያ በጨለማ ምን አይቶ ይወስን? የቀኙን መረጠ፡፡
የማሪየስ ሁለት እጆችና ጭንቅላት ወደኋላ ተንጠልጥለዋል፡፡ ዣን ቫልዣ የልጁን ሁለት እግሮች ከፊት አድርጎ ትከሻው ላይ ነው የተሸከመው::የልጁን እግሮች በግራ እጁ ጥርቅም አድርጎ ይዞ በቀኙ እጁ ከፊት ለፊቱ
ያለውን እየዳበሰ ይሄዳል:: የተቻለውን ያህል እየፈጠነ በቶሉ ነው የሚራመደው:: የማሪየስና የዣን ቫልዣ አንገት በማሪየስ የረጋ ደም ተጣብቀዋል::
ጥቂት እንደተጓዙ የደረሱበት ሥፍራ ጥቂት ሰፋ ያለ ነበር፡፡ ባለፈው ቀን የዘነበው ዝናብ ውሃ ተሟጥጦ ስላላለቀ ዣን ቫልዣ የሚራመድበት ውሃ መጠን ከፍ አለ፡፡ በቶሎ ለመራመድ ስላስቸገረው በጣም ዝግ አለ፡፡
አንዳንዴ በአንድ እጁ ግድግዳውን ተደግፎ ካልሆነ እግሩን ማነቃነቅ አይችልም::በጭንቀት ተውጦ አልቆመም:: እምነቱን ፈጣሪ ላይ ጥሎ በቀንድ አውጣ ጉዞ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ግን የፈሳሽ መጠን ከፍ ብሎ ከጉልበቱ አለፈ::
ጥቂት ሲቆይ ከዚያም ከፍ አለ፡፡ ለመመለስና ቀደም ሲል የተወውን የግራ መንገድ ለመያዝ አስቦ «አይሆንም» ብሎ በመወሰን አሁንም ወደፊት ቀጠለ፡፡ ብዙ በተጓዘ ቁጥር ድካም እየጠናበት ሄደ::
ዣን ቫልገዥ ከረሃብ፣ ከሸክምና ከመንገዱ ይበልጥ የጎዳው ውሃ
ጥሙ ነበር፡፡ ውሃ ላይ እየተራመደ ውሃውን ሊጠጣው ስለማይችል ባህር ላይ እየተጓዘ በውሃ ጥም እንደሚቃጠል ሰው እርሱም በውሃ ጥም ተቃጠለ፤ ነደደ፡፡ ምንም እንኳ እድሜው እየገፋ ቢሄድም ጉልበቱ አልተቀነሰም::
አሁን ግን ሸክሙና የውሃ ጥሙ ያንን ብርቱ ጉልበት አሳጣው:: ጉልበቱ እየቀነሰ ሲሄድ የተሸከመው ሰው ክብደት የጨመረ መሰለው:: እንደ
ጥምብ ስለከበደው «ማሪየስ ሞቶ ሊሆን ይችላል» ሲል አሰበ፡፡ ሰዓቱ ወደ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ይሆናል።
አሁን የደረሰበት አካባቢ የፈሳሹ ጥልቀት ከመጨመሩም በላይ የጉኑም ርቀት ሰፍቶአል:: ከመሃል ሆኖ የግራና ቀኝ ግድግዳ ሊነካ አልቻለም::መንታ መንገድ ላይ ስለደረሰ አሁን ወደ ግራ ታጠፈ:: ውሃ ያልደረሰበት ሾል ያለ ግድግዳ በማየቱ ማሪየስን ከዚያ አሳረፈው፡፡ በአካባቢው ቀዳዳ
ነገር ስለነበረና በዚያ በኩል ብርሃን በመግባቱ ማሪየስን ያሳረፈበት ግምብ በጉልህ እንኳን ባይሆን በጭላንጭል ታየው:: እንዲያውም በደም የተጨማለቀውን የማሪየስን ፊት ለማየት ቻለ፡፡ ማሪየስ ዓይኑን ጨፍኖአል።ፀጉሩ ያልታጠበ የቀለም ብሩሽ ይመስል በረጋ ደም ተቆጣጥሮ ግምባሩን ሸፍኖታል፡፡
ከአፉ ዳርና ዳር የሳሳ የረጋ ደም ይታያል:: እጁ ተዝለፍልፎ
ከግምቡ ላይ ተንጠልጥሎአል፡፡ በተመታበት አካባቢ በረጋ ደም ሸሚዙና ኮቱ ከሰውነቱ ጋር ተጣብቆአል፡፡ ዣን ቫልዣ የማሪየስን ልብስ ከፋፍቶ
በእጁ የማሪየስን ልብ ትርታ አዳመጠ፡፡ ልቡ ይመታል፡፡ ሕይወቱ አለች ማለት ነው:: ዣን ቫልዣ የራሱን ሸሚዝ ቀድዶ የማሪየስን ቁስል ከጠራረገ
በኋላ በተቻለው ሁሉ ጠበቅ አድርጎ አሰረለት::
ኪሱን ሲደባብስ ሁለት ነገሮችን አገኘ፡፡ እነርሱም የማሪየስ የማስታወሻ ደብተርና ካለፈው ቀን ጀምሮ ኪሱ ውስጥ የተረሳው ቁራሽ ዳቦ ነበሩ፡፡ደረቁን ዳቦ ዣን ቫልዣ በላው:: የማስታወሻ ደብተሩን በጭላንጭል ብርሃን
ወደሚገኝበት አቅጣጫ ወስዶ ተመለከተው:: ከመጀመሪያው ገጽ ላይ የሚከተለው ማስታወሻ ተጽፎ ነበር::
«ስሜ ማሪየስ ፓንትመርሲ ይባላል:: ሬሣዬን ለአያቴ ለመሴይ
ጊልኖርማንድ ውሰዱና ስጡልኝ:: የአያቴ እድራሻ ካልቬር ከሚባል ጎዳና የቤት ቁጥር ስድስት ነው::
ዣን ቫልዣ ለተወሰነ ጊዜ ፈዝዞ ቀረ:: የማስታወሻ ደብተሩን ከማሪየስ ኪስ ውስጥ መልሶ አስቀመጠው:: ዳቦውን ስለቀመሰ ነፍሱ ትንሽ መለስ አለች ማሪየስን አንስቶ እንደገና ተሸከመው:: የማሪየስን ጭንቅላት ቀስ
ብሎ ከቀኝ ትከሻው ላይ አሳረፈው:: ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ከአንድ ከተወሰነ ሥፍራ ሲደርስ ከባድ ጨለማ ሆነበት:: አልፎ አልፎ ይታዩ የነበሩት ለአየር
መግቢያ እየተባለ የሚሠሩት ቀዳዳዎች ጨርሰው ስለጠፉ እግር ቢወጉ እንኳን የማይታይ ጨለማ ሰፈነ፡፡
ዣን ቫልዣ አሁን የደረሰበት መሬት በደለል የተሞላ መሆኑን
ተገነዘበ፡፡ ከላይ ግን በውሃ ተሞልቷል፡፡ ደለሉ እግሩን ያዘው:: ማሪየስ እየደከመ ሄደ፡፡ እርሱም ቢሆን ጉልበቱ አልቆ በጣም እየደከመ ነው:: ባለው ኃይል በመጠቀም ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ከሥር የዘቀጠው ጭቃ መጠን
እየጨመረ ሄደ፡፡ እስከ ጉልበቱ ሊደርስ ምንም ያህል አልቀረውም፡፡እየጨመረ የሄደው ጭቃው ብቻ ሳይሆን ወሃውም ስለነበር እስከወገቡ ደረሰ፡፡ ሆኖም ዣን ቫልዣ አሁንም ተስፋ ሳይቆረጥ ያንን ከሞት አፋፍ
የደረሰውን ሰው ተሸክሞ ተጓዘ፡፡
የውሃው መጠን ከብብቱ ሥር ደረሰ፡፡ የመንቀሳቀሱ ጉዳይ በጣም ችግር ሆነ፡፡ ግን ማሪየስን በሁለት እጁ አጥብቆ ይዞ አሁንም ተስፋ ሳይቆርጥ ባለው ኃይል በመጠቀም ጥቂት ከተራመደ በኋላ ከነበረበት ቆም
ብሎ ትንፋሹን ዋጥ አደረገ፡ እንደገና ጉዞውን ቀጠለ፡፡ የውሃው መጠን ከትከሻው ደረሰ፡፡ ማሪየስ እንዳይታፈን ከእግሩ ወደ ውሃው ጎተት በማድረግ
ከአንገቱ ቀና አደረገው:: ራሱም ቢሆን አንጋጣ ነው የሚራመደው::
ድንገት እግሩ ከአንድ ነገር ጋር ተጋጨ፡፡ ያልተጋጨው እግሩን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ከብርሃን ወደ ጨለማ
ዣን ቫልዣ ከፓሪስ ከተማ ባህር ውስጥ ነው የገባው:: ከባህር ውስጥ የገባ ዋናተኛ ሊጠፋ እንደሚችል ሁሉ እርሱም ሊጠፋ ይችላል፡፡ ከብርሃን ወደ ጨለማ ነው የተጓዘው:: በእጁ ፋኖስ ወይም ሌላ መብራት የለም፡፡
ሆኖም ከሞት አፋፍ ደርሶ የነበረው ዣን ቫልዣ ማንም ሊደርስበት ከማይችል
ሥፍራ ነው የሄደው:: ከመሃል ከተማ ወጥቶ ሰው ከማይደርስበት ገጠር ነው የገባው ለማለት ይቻላል፡፡ ከጫጫታና ከሁካታ ወደ ፀጥታ ነው የተሸጋገረው:: ከሞት ወደ ደኅንነት ነው የተዛወረው:: እንዲህ ያለው ነው መልካም አጋጣሚ የሚባለው:: ተፈጥሮ ሆን ብላ ዣን ቫልዣን ለማዳን ያዘጋጀችው ይመስላል፡፡
ማሪየስ ነቅነቅ እንኳን አላለም፡፡ ይሙት ወይም በሕይወት ይኑር
አይታወቅም፡፡ መሬት ሊወድቅ ሲል ዣን ቫልዣ ካነሳው ጀምሮ ሕሊናውን እንደሳተ ነው::
ዣን ቫልዣ ያለበትን ሥፍራ ለማወቅ መጀመሪያ ቀኝ እጁን፤ በኋላም ግራ እጁን ወደ ጐን ዘረጋ፡፡ በሁለቱም በኩል ግድግዳ ነካ፡፡ የቆመበትን ቦታ ጎን ስፋት በዚህ አረጋገጠ፡፡ ቀስ እያለ ወደፊት ተራመደ፡፡ መሬቱ ይርጠብ
እንጂ የተነጠፈ ድንጋይ በመሆኑ ቀዳዳ ነገር እንደሌለው ተረዳ፡፡ ስለዚህ የየቆሻሻ መውረጃው አሠራር እንዴት እንደሆነ ስለሚያውቅ ምን ውስጥ
እንደገባ ያውቃል፡፡
አሁን ካለበት አካባቢ እጅግ በጣም አነስተኛ የሆነ ብርሃን በዚያች በብረት ክዳን በኩል ይገባ ስለነበር እንደ ውጋገን ያለ ነገር ይታያል፡፡ስለቦታው ለማወቅ ፈልጎ ጥቂት ወደፊት በተራመደ ጊዜ ግን ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ ሆነበት:: ማሪየስን እንደገና ተሸክሞ ሃምሳ እርምጃ ያህል ከተራመደ
በኋላ ቆም አለ፡፡ ከቆሻሻ መውረጃ መንታ መንገድ ላይ ደረሰ፡፡ እንዲያውም ከግድግዳ ጋር ሊጋጭ ሲል ለትንሽ ነው የዳነው:: የቀኙን ወይስ የግራውን
መንገድ ይከተል? በዚያ በጨለማ ምን አይቶ ይወስን? የቀኙን መረጠ፡፡
የማሪየስ ሁለት እጆችና ጭንቅላት ወደኋላ ተንጠልጥለዋል፡፡ ዣን ቫልዣ የልጁን ሁለት እግሮች ከፊት አድርጎ ትከሻው ላይ ነው የተሸከመው::የልጁን እግሮች በግራ እጁ ጥርቅም አድርጎ ይዞ በቀኙ እጁ ከፊት ለፊቱ
ያለውን እየዳበሰ ይሄዳል:: የተቻለውን ያህል እየፈጠነ በቶሉ ነው የሚራመደው:: የማሪየስና የዣን ቫልዣ አንገት በማሪየስ የረጋ ደም ተጣብቀዋል::
ጥቂት እንደተጓዙ የደረሱበት ሥፍራ ጥቂት ሰፋ ያለ ነበር፡፡ ባለፈው ቀን የዘነበው ዝናብ ውሃ ተሟጥጦ ስላላለቀ ዣን ቫልዣ የሚራመድበት ውሃ መጠን ከፍ አለ፡፡ በቶሎ ለመራመድ ስላስቸገረው በጣም ዝግ አለ፡፡
አንዳንዴ በአንድ እጁ ግድግዳውን ተደግፎ ካልሆነ እግሩን ማነቃነቅ አይችልም::በጭንቀት ተውጦ አልቆመም:: እምነቱን ፈጣሪ ላይ ጥሎ በቀንድ አውጣ ጉዞ መንገዱን ቀጠለ፡፡ ግን የፈሳሽ መጠን ከፍ ብሎ ከጉልበቱ አለፈ::
ጥቂት ሲቆይ ከዚያም ከፍ አለ፡፡ ለመመለስና ቀደም ሲል የተወውን የግራ መንገድ ለመያዝ አስቦ «አይሆንም» ብሎ በመወሰን አሁንም ወደፊት ቀጠለ፡፡ ብዙ በተጓዘ ቁጥር ድካም እየጠናበት ሄደ::
ዣን ቫልገዥ ከረሃብ፣ ከሸክምና ከመንገዱ ይበልጥ የጎዳው ውሃ
ጥሙ ነበር፡፡ ውሃ ላይ እየተራመደ ውሃውን ሊጠጣው ስለማይችል ባህር ላይ እየተጓዘ በውሃ ጥም እንደሚቃጠል ሰው እርሱም በውሃ ጥም ተቃጠለ፤ ነደደ፡፡ ምንም እንኳ እድሜው እየገፋ ቢሄድም ጉልበቱ አልተቀነሰም::
አሁን ግን ሸክሙና የውሃ ጥሙ ያንን ብርቱ ጉልበት አሳጣው:: ጉልበቱ እየቀነሰ ሲሄድ የተሸከመው ሰው ክብደት የጨመረ መሰለው:: እንደ
ጥምብ ስለከበደው «ማሪየስ ሞቶ ሊሆን ይችላል» ሲል አሰበ፡፡ ሰዓቱ ወደ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ይሆናል።
አሁን የደረሰበት አካባቢ የፈሳሹ ጥልቀት ከመጨመሩም በላይ የጉኑም ርቀት ሰፍቶአል:: ከመሃል ሆኖ የግራና ቀኝ ግድግዳ ሊነካ አልቻለም::መንታ መንገድ ላይ ስለደረሰ አሁን ወደ ግራ ታጠፈ:: ውሃ ያልደረሰበት ሾል ያለ ግድግዳ በማየቱ ማሪየስን ከዚያ አሳረፈው፡፡ በአካባቢው ቀዳዳ
ነገር ስለነበረና በዚያ በኩል ብርሃን በመግባቱ ማሪየስን ያሳረፈበት ግምብ በጉልህ እንኳን ባይሆን በጭላንጭል ታየው:: እንዲያውም በደም የተጨማለቀውን የማሪየስን ፊት ለማየት ቻለ፡፡ ማሪየስ ዓይኑን ጨፍኖአል።ፀጉሩ ያልታጠበ የቀለም ብሩሽ ይመስል በረጋ ደም ተቆጣጥሮ ግምባሩን ሸፍኖታል፡፡
ከአፉ ዳርና ዳር የሳሳ የረጋ ደም ይታያል:: እጁ ተዝለፍልፎ
ከግምቡ ላይ ተንጠልጥሎአል፡፡ በተመታበት አካባቢ በረጋ ደም ሸሚዙና ኮቱ ከሰውነቱ ጋር ተጣብቆአል፡፡ ዣን ቫልዣ የማሪየስን ልብስ ከፋፍቶ
በእጁ የማሪየስን ልብ ትርታ አዳመጠ፡፡ ልቡ ይመታል፡፡ ሕይወቱ አለች ማለት ነው:: ዣን ቫልዣ የራሱን ሸሚዝ ቀድዶ የማሪየስን ቁስል ከጠራረገ
በኋላ በተቻለው ሁሉ ጠበቅ አድርጎ አሰረለት::
ኪሱን ሲደባብስ ሁለት ነገሮችን አገኘ፡፡ እነርሱም የማሪየስ የማስታወሻ ደብተርና ካለፈው ቀን ጀምሮ ኪሱ ውስጥ የተረሳው ቁራሽ ዳቦ ነበሩ፡፡ደረቁን ዳቦ ዣን ቫልዣ በላው:: የማስታወሻ ደብተሩን በጭላንጭል ብርሃን
ወደሚገኝበት አቅጣጫ ወስዶ ተመለከተው:: ከመጀመሪያው ገጽ ላይ የሚከተለው ማስታወሻ ተጽፎ ነበር::
«ስሜ ማሪየስ ፓንትመርሲ ይባላል:: ሬሣዬን ለአያቴ ለመሴይ
ጊልኖርማንድ ውሰዱና ስጡልኝ:: የአያቴ እድራሻ ካልቬር ከሚባል ጎዳና የቤት ቁጥር ስድስት ነው::
ዣን ቫልዣ ለተወሰነ ጊዜ ፈዝዞ ቀረ:: የማስታወሻ ደብተሩን ከማሪየስ ኪስ ውስጥ መልሶ አስቀመጠው:: ዳቦውን ስለቀመሰ ነፍሱ ትንሽ መለስ አለች ማሪየስን አንስቶ እንደገና ተሸከመው:: የማሪየስን ጭንቅላት ቀስ
ብሎ ከቀኝ ትከሻው ላይ አሳረፈው:: ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ከአንድ ከተወሰነ ሥፍራ ሲደርስ ከባድ ጨለማ ሆነበት:: አልፎ አልፎ ይታዩ የነበሩት ለአየር
መግቢያ እየተባለ የሚሠሩት ቀዳዳዎች ጨርሰው ስለጠፉ እግር ቢወጉ እንኳን የማይታይ ጨለማ ሰፈነ፡፡
ዣን ቫልዣ አሁን የደረሰበት መሬት በደለል የተሞላ መሆኑን
ተገነዘበ፡፡ ከላይ ግን በውሃ ተሞልቷል፡፡ ደለሉ እግሩን ያዘው:: ማሪየስ እየደከመ ሄደ፡፡ እርሱም ቢሆን ጉልበቱ አልቆ በጣም እየደከመ ነው:: ባለው ኃይል በመጠቀም ጉዞውን ቀጠለ፡፡ ከሥር የዘቀጠው ጭቃ መጠን
እየጨመረ ሄደ፡፡ እስከ ጉልበቱ ሊደርስ ምንም ያህል አልቀረውም፡፡እየጨመረ የሄደው ጭቃው ብቻ ሳይሆን ወሃውም ስለነበር እስከወገቡ ደረሰ፡፡ ሆኖም ዣን ቫልዣ አሁንም ተስፋ ሳይቆረጥ ያንን ከሞት አፋፍ
የደረሰውን ሰው ተሸክሞ ተጓዘ፡፡
የውሃው መጠን ከብብቱ ሥር ደረሰ፡፡ የመንቀሳቀሱ ጉዳይ በጣም ችግር ሆነ፡፡ ግን ማሪየስን በሁለት እጁ አጥብቆ ይዞ አሁንም ተስፋ ሳይቆርጥ ባለው ኃይል በመጠቀም ጥቂት ከተራመደ በኋላ ከነበረበት ቆም
ብሎ ትንፋሹን ዋጥ አደረገ፡ እንደገና ጉዞውን ቀጠለ፡፡ የውሃው መጠን ከትከሻው ደረሰ፡፡ ማሪየስ እንዳይታፈን ከእግሩ ወደ ውሃው ጎተት በማድረግ
ከአንገቱ ቀና አደረገው:: ራሱም ቢሆን አንጋጣ ነው የሚራመደው::
ድንገት እግሩ ከአንድ ነገር ጋር ተጋጨ፡፡ ያልተጋጨው እግሩን
👍8❤1👏1
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ሐኪሙ እስኪመጣ ማሪየስ ከተኛበት አልተንቀሳቀሰም:: አክስቱ ግን ከመኝታዋ ተነስታ ከአጠገቡ ቁጭ ብላለች:: «ወይኔ ጉዴ ፧ አምላኬ ከዚህ አውጣኝ» ብሎ ከማልቀስና ከወዲያ ወዲህ ከመንቆራጠጥ ሌላ ያደረገችው
ነገር አልነበረም::
ሐኪሙ ማሪየስን መረመረው:: እስትንፋሱ አለች፡፡ በጀርባው አስተኝቶ ቁስል እንደሌለበት ተረዳ፡፡ ልብሱንተ ሲያወልቁለት አክስትየው ወደ ውጭ ወጣች:: መቁጠሪያዋን ይዛ ትጸልይ ጀመር፡፡
ከጎድኑ ላይ ቁስል አለ፡፡ ግን በጣም ወደ ውስጥ የገባ ቁስል አይደለም::እጁም ላይ በጐራዴ ተመትቶአል፡፡ ከጭንቅላቱም ላይ እንዲሁ በመወጋቱ የደማ ቁስል አለ፡፡ ከግምባሩ ላይ አጥንቱ ተሰብሮ እንደሆነ ሐኪሙ በዝግታ
ነካካው:: ለመለየት አቃተው:: ሆኖም ሐኪሙን ከዚህ ሁሉ ይበልጥ ያሳሰበው የማሪየስ ነፍስ አለማወቅ ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ወንዶች ነፍሳቸውን ከሳቱ በዚያው ይቀራሉ እንጂ አይነቁም:: አሁን ታዲያ ማሪየስ ይነቃል ወይስ አይነቃም ሲል ተጨነቀ:: ብዙ ደም ስለፈሰሰው ሰውነቱ ዝሉአል::
ሴቶቹ የማሪየስን ቁስል ካጣጠቡ በኋላ ሐኪሙ እያዠ የሚወጣውን
ደም አቆመው፡፡ ጭንቅላቱን በቃገቃዛ ውሃና ሳሙና አጠቡት፡፡ ሐኪሙ የማሪየስን ግምባር እያሻሸ ሲጠራርግ በር ተከፈተ፡፡ በጣም ደነገጠና የገረጣ
ፊት ብቅ አለ፡፡
አያቱ ነበሩ፡፡ ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠ አንገታቸውን ብቻ ወደ ውስጥ በማስገባት ተመለከቱ፡፡ የሌሊት ልብስ ነው የለበሱት:: መቃብር
እንጂ ደህና ነገር የሚያዩ አይመስሉም፡፡ ማሪየስ አልጋ ላይ ተዘርሮና አዓይኑን ጨፍኖ ነው ያዩት:: እስከ መታወቂያው ራቁቱን ነው የተኛው::በጥፊ እንደ ተመታ ሰው ክው እንዳሉ ወደ አልጋው ተጠጉ:: ልባቸው በኃይል ይመታል፡፡
«ማሪየስ!» ሲሉ በዝግታ ተጣሩ፡፡
«አባባ» አለች አንደኛዋ ሠራተኛ «አሁን ነው ሰዎች ይዘውት
የመጡት:: ከጦርነቱ ቦታ ነበር ብለዋል፡፡›
«ሞቷል!» ሲሉ ሽማግሌው መጮህ ጀመሩ:: «ዶክተር» አሉ፤ «አንተ ነህ ሁሉንም የምታውቀው:: አንድ ነገር ብቻ ንገረኝ:: ሞቷል ፤ አይደል?»
ሐኪሙ በጣም ተጨንቆ ስለነበር መልስም አልሰጣቸውም::
ሽማግሌው እያጨበጨቡ ይስቁ ጀመር፡፡ ተደጋግሞ እንደተባለው
«ማሽላ እያረረ ይስቃል» ይሉ የለ!
«ሞቷል! ሞቷል! ከዚያ ከምሽጋቸው ወስጥ ነው የተገደለው! ሳንታረቅ! በጥላቻ ዓይን እየተመለከተኝ ነዋ ሕይወቱ ያለፈችው! ይኼ ርኩስ! ሞቶ ሬሣው ይምጣልኝ! ይኼ ነዋ የእኔ እጣ ፋንታ! ሞቷል! ሞቷል!»
ሐኪመ ማሪየስን ትቶ ወደ መሴይ ጊልኖርማንድ ሄደ:: ሰውዬውም
ዞር ብለው በአበጠ ዓይናቸው ተመለከቱት::
«ይቅርታህን ዝም እላለሁ፡፡ ምንም እንኳን ብዘ ሰው ከአጠገቤ
ሲለይ ባይም የአሁኑ በዚህ እድሜዬ አላስችል ስላለኝ ነው:: ብቻ በማያገባቸው ነገር ይገቡ፤ ይለፈልፉና ውጤታቸው ይሄ በመሆኑ አሳዘነኝ፡፡ ይጽፋሉ፤
ይናገራሉ፤ ወደፊት፤ ወደኋላ፤ አዲስ ሕይወት፧ ነፃነት፣ መብት፧ ሌላም ሌላም እያሉ ይጮሁና ሬሣ ይዘውልን ይመጣሉ፡፡ ብቻ ምን ይሆናል ይቅር! ልቻለው፤ አይ ልጄ ማሪየስ! ገደለህ፤ ከእኔ በፊት ሞትክ፣ ያሳደግሁት ልጄ እኮ ነው! ገና አንድ ፍሬ ሆኖ ሳለ እኮ ነው እኔ ያረጀሁት:: ታዲያ እኔ
ቆሜ እርሱ ይሙት:: እርሱ የፈጨውን አፈር እኮ አብረን አብኩተናል፡፡ እርሱ በሕፃንነቱ እኔ በስተርጅናዬ! ብቻ ምን ይሆናል ተዉት፡፡ ጠዋት ጠዋት ከመኝታ ክፍሌ እየሮጠ ሲመጣ፣ ስቆጣው፣ እርሱ ሲስቅ፣ የማታ
ማታውማ ከላዬ ላይ ካልወጣሁ ሲል «ኧረ እኔ አልችልም» እያልኩ
ስቆጣው ፧ የጨዋታ መሆኑ እየገባው አይቆጣ! ኧረ ስንቱን ላንሳው! የሕይወቴ ብርሃን ነበር፡፡ እንደዚህ ልጅ የሚወደድ ፧ አንጀት የሚበላ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም::»
ጠጋ ብለው አዩት:: አሁንም ነቅነቅ አይልም:: «እነዚህ አረመኔዎች»
ሲሉ ጮሁ:: የማሪየስ የዓይን ሽፋን ተነቃነቀ፡፡ በፈዘዘ ዓይን አያቸው፡፡
«ማሪየስ» ሲሉ ሽማግሌው ተናገሩ፡: «ማሪየስ፤ የእኔ ጌታ! ልጄ! ሕይወትህ አለ? አየኸኝ እኮ! ተመስገን፣ ተመስገን አምላኬ!»
ነፍሳቸውን ስተው ከመሬት ተዘረሩ::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣቬር መስመር ሲለቅ
ዣቬር እያዘገመ ከገዣን ቫልገዣ ቤት ወጥቶ ሄደ:: የሚራመደው
እያቀረቀረ ነው:: በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ እጁን ወደኋላ አድርጎ ተራመደ:: ፀጥ ካለው አውራ ጎዳና ውስጥ ደረሰ፡፡ ዝም ብሉ ብቻ ወደፊት ነው የሚሄደው:: ወደ ሳይን ወንዝ የሚወስደውን መንገድ ይዞ ነው የሚጓዘው::
ትልቅ ድልድይ ካለበት ስለደረሰ የድልድዩን አግዳሚ ብረት ተደግፎ
ቆመ:: በጣቶቹ ሪዙን እያፍተለተለ አገጩን በእጆቹ ደግፎ ነው የቆመው::በሀሳብ ነጉዷል።
ሰውነቱ ውስጥ አዲስ ነገር፣ አንድ ዓይነት ለውጥ፣ እረፍት የሚነሳ
ስቃይ እየተፈራረቀ ነው:: ራሱን ማለት የግል ሕይወቱን ይመረምር
ጀመር፡፡
በሚያሳዝን ሁኔታ ዣቬር እየተሰቃየ ነው:: ዣቬር ልክ አልነበረም::ጥቂት ሰዓት አለፈ:: አንጎሉ ተረበሽ፣ ሁለም ነገር ተመስቃቀለበት::ስለሥራው የነበረው ደንዳና እምነት ላላ፡፡ ህሊናው ውስጥ የነበረው
የማይደፈር ሥልጣን ዋዠቀ፡፡ ይህን ሁኔታ ከራሱ ሊሸሽገው አልቻለም:: ይች ካልጠበቀው ቦታና ባላሰበው ጊዜ ዣን ቫልዣን ከወንዞ ዳር አገኘው:: ዣን
ቫልዣን ሲያገኘው ጥምቡን መልሶ እንዳገኘ ተኩላ ወይም የጠፋበትን ጌታ እንዳገኘ ውሻ ዓይነት ስሜት ነበረው::
ሁለት ዋና መንገዶችን አየ:: ከሁለቱ ዋና መንገዶች የትኛው ነው ! እውነተኛ? ልቡ ፈራ:: እድሜ ልኩን ያየው የነበረውና ትክከለኛ ነው ብሎ የሚያምንበት አንድ መንገድ ብቻ ነበር፡፡ አሁን ግን ሁለት ሆኑበት፡፡ ጨርሶ ግራ ተጋባ፡፡ ለማንኛውም ከህሊናው ውስጥ ምን ይተራመስ እንደነበር
አረጋግጦ ለመጻፍ ትንሽ ያስቸግራል::
አንድ ነገር ግን በጣም አስገርሞታል፡፡ ይኸውም የእርሱ ሕይወት በዣን ቫልዣ ምክንያት መትረፉንና የዣን ቫልዣ ሕይወት ደግሞ ከእርሱ ምህረት ማግኘቱ ነበር፡፡ የት ነው ያለው? አሁን ምን ይሥራ? ዣን ቫልዣን ይርዳው? ትክክል ሥራ አይሆንም:: ዣን ቫልዣ ነፃ ይውጣ? ስህተት ይሆናል፡፡ ታዲያ ከከፍተኛ ማዕረግ ላይ ያለ ሰው ከአንድ እስረኛ
ይነስ? በሌላ አንፃር ደግሞ ወንጀለኛ ከሕግ በላይ ሆኖ ሕግን ሲረግጥ? በሁለቱም መንገድ ቢሆን ለእርሱ ለዣቬር ውርደት ነው::
በሕይወት ዘመናችን የምንደርስባቸወ እንደዚህ ያለ ምርጫ የሚያሳጡና መፍትሔ ከሌለው ነገር ጫፍ የሚያደርስ አጋጣሚዎች አሉ:: እነዚህ አጋጣሚዎች መያዣ ወይም መጨበጫ የሚያሳጡ ናቸው::
ዣቬር ከእንደዚያ ያለ ፈተና ውስጥ ነበር የገባው::
የጭንቀቱ መነሻ ከአሳብ ውስጥ እንዲገባ መገደዱ ነው:: እነዚያ
ተቃራኒ አሳቦች ናቸው እንዲጨነቅና እንዲያስብ ያደረጉት: አሳብና ጭንቀት
ለእርሱ እንግዳ ነገሮች ናቸው:: አዲስ በመሆናቸውም አሰቃዩት፡፡ እርሱ የለመደው አንድን አሳብ «ወደፊት» ማራመድ ብቻ ነበር:: አሳብ ጭንቅላታችን ውስጥ በሚገባበት ጊዜ ለአንድ ድርጊት የሚገፋፋን የአመፅ ስሜት በውስጣችን አለ፡፡ ይህ ዓይነት ስሜት ስላደረበት ዣቬር ተናደደ፡፡
ታዲያ ከምን ውሳኔ ላይ ይድረስ? ያለው ምርጫ አንድ ሲሆን
ይኸውም ወደ ዣን ቫልዣ ቤት ተመልሶ ሄዶ ዣን ቫልዣን ማሰር ነው፡፡ ከአንድ የፖሊስ አዛዥ የሚጠበቀውም ይኸው ነው፡፡ ግን እንዴት አድርጎ! አይችልም፡፡ ይህን እንዳይፈጽም መንገዱን የዘጋበት ነገር አለ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...ሐኪሙ እስኪመጣ ማሪየስ ከተኛበት አልተንቀሳቀሰም:: አክስቱ ግን ከመኝታዋ ተነስታ ከአጠገቡ ቁጭ ብላለች:: «ወይኔ ጉዴ ፧ አምላኬ ከዚህ አውጣኝ» ብሎ ከማልቀስና ከወዲያ ወዲህ ከመንቆራጠጥ ሌላ ያደረገችው
ነገር አልነበረም::
ሐኪሙ ማሪየስን መረመረው:: እስትንፋሱ አለች፡፡ በጀርባው አስተኝቶ ቁስል እንደሌለበት ተረዳ፡፡ ልብሱንተ ሲያወልቁለት አክስትየው ወደ ውጭ ወጣች:: መቁጠሪያዋን ይዛ ትጸልይ ጀመር፡፡
ከጎድኑ ላይ ቁስል አለ፡፡ ግን በጣም ወደ ውስጥ የገባ ቁስል አይደለም::እጁም ላይ በጐራዴ ተመትቶአል፡፡ ከጭንቅላቱም ላይ እንዲሁ በመወጋቱ የደማ ቁስል አለ፡፡ ከግምባሩ ላይ አጥንቱ ተሰብሮ እንደሆነ ሐኪሙ በዝግታ
ነካካው:: ለመለየት አቃተው:: ሆኖም ሐኪሙን ከዚህ ሁሉ ይበልጥ ያሳሰበው የማሪየስ ነፍስ አለማወቅ ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ወንዶች ነፍሳቸውን ከሳቱ በዚያው ይቀራሉ እንጂ አይነቁም:: አሁን ታዲያ ማሪየስ ይነቃል ወይስ አይነቃም ሲል ተጨነቀ:: ብዙ ደም ስለፈሰሰው ሰውነቱ ዝሉአል::
ሴቶቹ የማሪየስን ቁስል ካጣጠቡ በኋላ ሐኪሙ እያዠ የሚወጣውን
ደም አቆመው፡፡ ጭንቅላቱን በቃገቃዛ ውሃና ሳሙና አጠቡት፡፡ ሐኪሙ የማሪየስን ግምባር እያሻሸ ሲጠራርግ በር ተከፈተ፡፡ በጣም ደነገጠና የገረጣ
ፊት ብቅ አለ፡፡
አያቱ ነበሩ፡፡ ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠ አንገታቸውን ብቻ ወደ ውስጥ በማስገባት ተመለከቱ፡፡ የሌሊት ልብስ ነው የለበሱት:: መቃብር
እንጂ ደህና ነገር የሚያዩ አይመስሉም፡፡ ማሪየስ አልጋ ላይ ተዘርሮና አዓይኑን ጨፍኖ ነው ያዩት:: እስከ መታወቂያው ራቁቱን ነው የተኛው::በጥፊ እንደ ተመታ ሰው ክው እንዳሉ ወደ አልጋው ተጠጉ:: ልባቸው በኃይል ይመታል፡፡
«ማሪየስ!» ሲሉ በዝግታ ተጣሩ፡፡
«አባባ» አለች አንደኛዋ ሠራተኛ «አሁን ነው ሰዎች ይዘውት
የመጡት:: ከጦርነቱ ቦታ ነበር ብለዋል፡፡›
«ሞቷል!» ሲሉ ሽማግሌው መጮህ ጀመሩ:: «ዶክተር» አሉ፤ «አንተ ነህ ሁሉንም የምታውቀው:: አንድ ነገር ብቻ ንገረኝ:: ሞቷል ፤ አይደል?»
ሐኪሙ በጣም ተጨንቆ ስለነበር መልስም አልሰጣቸውም::
ሽማግሌው እያጨበጨቡ ይስቁ ጀመር፡፡ ተደጋግሞ እንደተባለው
«ማሽላ እያረረ ይስቃል» ይሉ የለ!
«ሞቷል! ሞቷል! ከዚያ ከምሽጋቸው ወስጥ ነው የተገደለው! ሳንታረቅ! በጥላቻ ዓይን እየተመለከተኝ ነዋ ሕይወቱ ያለፈችው! ይኼ ርኩስ! ሞቶ ሬሣው ይምጣልኝ! ይኼ ነዋ የእኔ እጣ ፋንታ! ሞቷል! ሞቷል!»
ሐኪመ ማሪየስን ትቶ ወደ መሴይ ጊልኖርማንድ ሄደ:: ሰውዬውም
ዞር ብለው በአበጠ ዓይናቸው ተመለከቱት::
«ይቅርታህን ዝም እላለሁ፡፡ ምንም እንኳን ብዘ ሰው ከአጠገቤ
ሲለይ ባይም የአሁኑ በዚህ እድሜዬ አላስችል ስላለኝ ነው:: ብቻ በማያገባቸው ነገር ይገቡ፤ ይለፈልፉና ውጤታቸው ይሄ በመሆኑ አሳዘነኝ፡፡ ይጽፋሉ፤
ይናገራሉ፤ ወደፊት፤ ወደኋላ፤ አዲስ ሕይወት፧ ነፃነት፣ መብት፧ ሌላም ሌላም እያሉ ይጮሁና ሬሣ ይዘውልን ይመጣሉ፡፡ ብቻ ምን ይሆናል ይቅር! ልቻለው፤ አይ ልጄ ማሪየስ! ገደለህ፤ ከእኔ በፊት ሞትክ፣ ያሳደግሁት ልጄ እኮ ነው! ገና አንድ ፍሬ ሆኖ ሳለ እኮ ነው እኔ ያረጀሁት:: ታዲያ እኔ
ቆሜ እርሱ ይሙት:: እርሱ የፈጨውን አፈር እኮ አብረን አብኩተናል፡፡ እርሱ በሕፃንነቱ እኔ በስተርጅናዬ! ብቻ ምን ይሆናል ተዉት፡፡ ጠዋት ጠዋት ከመኝታ ክፍሌ እየሮጠ ሲመጣ፣ ስቆጣው፣ እርሱ ሲስቅ፣ የማታ
ማታውማ ከላዬ ላይ ካልወጣሁ ሲል «ኧረ እኔ አልችልም» እያልኩ
ስቆጣው ፧ የጨዋታ መሆኑ እየገባው አይቆጣ! ኧረ ስንቱን ላንሳው! የሕይወቴ ብርሃን ነበር፡፡ እንደዚህ ልጅ የሚወደድ ፧ አንጀት የሚበላ ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም::»
ጠጋ ብለው አዩት:: አሁንም ነቅነቅ አይልም:: «እነዚህ አረመኔዎች»
ሲሉ ጮሁ:: የማሪየስ የዓይን ሽፋን ተነቃነቀ፡፡ በፈዘዘ ዓይን አያቸው፡፡
«ማሪየስ» ሲሉ ሽማግሌው ተናገሩ፡: «ማሪየስ፤ የእኔ ጌታ! ልጄ! ሕይወትህ አለ? አየኸኝ እኮ! ተመስገን፣ ተመስገን አምላኬ!»
ነፍሳቸውን ስተው ከመሬት ተዘረሩ::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዣቬር መስመር ሲለቅ
ዣቬር እያዘገመ ከገዣን ቫልገዣ ቤት ወጥቶ ሄደ:: የሚራመደው
እያቀረቀረ ነው:: በሕይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ እጁን ወደኋላ አድርጎ ተራመደ:: ፀጥ ካለው አውራ ጎዳና ውስጥ ደረሰ፡፡ ዝም ብሉ ብቻ ወደፊት ነው የሚሄደው:: ወደ ሳይን ወንዝ የሚወስደውን መንገድ ይዞ ነው የሚጓዘው::
ትልቅ ድልድይ ካለበት ስለደረሰ የድልድዩን አግዳሚ ብረት ተደግፎ
ቆመ:: በጣቶቹ ሪዙን እያፍተለተለ አገጩን በእጆቹ ደግፎ ነው የቆመው::በሀሳብ ነጉዷል።
ሰውነቱ ውስጥ አዲስ ነገር፣ አንድ ዓይነት ለውጥ፣ እረፍት የሚነሳ
ስቃይ እየተፈራረቀ ነው:: ራሱን ማለት የግል ሕይወቱን ይመረምር
ጀመር፡፡
በሚያሳዝን ሁኔታ ዣቬር እየተሰቃየ ነው:: ዣቬር ልክ አልነበረም::ጥቂት ሰዓት አለፈ:: አንጎሉ ተረበሽ፣ ሁለም ነገር ተመስቃቀለበት::ስለሥራው የነበረው ደንዳና እምነት ላላ፡፡ ህሊናው ውስጥ የነበረው
የማይደፈር ሥልጣን ዋዠቀ፡፡ ይህን ሁኔታ ከራሱ ሊሸሽገው አልቻለም:: ይች ካልጠበቀው ቦታና ባላሰበው ጊዜ ዣን ቫልዣን ከወንዞ ዳር አገኘው:: ዣን
ቫልዣን ሲያገኘው ጥምቡን መልሶ እንዳገኘ ተኩላ ወይም የጠፋበትን ጌታ እንዳገኘ ውሻ ዓይነት ስሜት ነበረው::
ሁለት ዋና መንገዶችን አየ:: ከሁለቱ ዋና መንገዶች የትኛው ነው ! እውነተኛ? ልቡ ፈራ:: እድሜ ልኩን ያየው የነበረውና ትክከለኛ ነው ብሎ የሚያምንበት አንድ መንገድ ብቻ ነበር፡፡ አሁን ግን ሁለት ሆኑበት፡፡ ጨርሶ ግራ ተጋባ፡፡ ለማንኛውም ከህሊናው ውስጥ ምን ይተራመስ እንደነበር
አረጋግጦ ለመጻፍ ትንሽ ያስቸግራል::
አንድ ነገር ግን በጣም አስገርሞታል፡፡ ይኸውም የእርሱ ሕይወት በዣን ቫልዣ ምክንያት መትረፉንና የዣን ቫልዣ ሕይወት ደግሞ ከእርሱ ምህረት ማግኘቱ ነበር፡፡ የት ነው ያለው? አሁን ምን ይሥራ? ዣን ቫልዣን ይርዳው? ትክክል ሥራ አይሆንም:: ዣን ቫልዣ ነፃ ይውጣ? ስህተት ይሆናል፡፡ ታዲያ ከከፍተኛ ማዕረግ ላይ ያለ ሰው ከአንድ እስረኛ
ይነስ? በሌላ አንፃር ደግሞ ወንጀለኛ ከሕግ በላይ ሆኖ ሕግን ሲረግጥ? በሁለቱም መንገድ ቢሆን ለእርሱ ለዣቬር ውርደት ነው::
በሕይወት ዘመናችን የምንደርስባቸወ እንደዚህ ያለ ምርጫ የሚያሳጡና መፍትሔ ከሌለው ነገር ጫፍ የሚያደርስ አጋጣሚዎች አሉ:: እነዚህ አጋጣሚዎች መያዣ ወይም መጨበጫ የሚያሳጡ ናቸው::
ዣቬር ከእንደዚያ ያለ ፈተና ውስጥ ነበር የገባው::
የጭንቀቱ መነሻ ከአሳብ ውስጥ እንዲገባ መገደዱ ነው:: እነዚያ
ተቃራኒ አሳቦች ናቸው እንዲጨነቅና እንዲያስብ ያደረጉት: አሳብና ጭንቀት
ለእርሱ እንግዳ ነገሮች ናቸው:: አዲስ በመሆናቸውም አሰቃዩት፡፡ እርሱ የለመደው አንድን አሳብ «ወደፊት» ማራመድ ብቻ ነበር:: አሳብ ጭንቅላታችን ውስጥ በሚገባበት ጊዜ ለአንድ ድርጊት የሚገፋፋን የአመፅ ስሜት በውስጣችን አለ፡፡ ይህ ዓይነት ስሜት ስላደረበት ዣቬር ተናደደ፡፡
ታዲያ ከምን ውሳኔ ላይ ይድረስ? ያለው ምርጫ አንድ ሲሆን
ይኸውም ወደ ዣን ቫልዣ ቤት ተመልሶ ሄዶ ዣን ቫልዣን ማሰር ነው፡፡ ከአንድ የፖሊስ አዛዥ የሚጠበቀውም ይኸው ነው፡፡ ግን እንዴት አድርጎ! አይችልም፡፡ ይህን እንዳይፈጽም መንገዱን የዘጋበት ነገር አለ፡፡
👍16
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የልጅ ልጅና አያቱ
ማሪየስ ለረጅም ጊዜ ስለታመመ መሞቱ ወይም በሕይወት መኖሩ
ሳይታወቅ ለረጅም ጊዜ ቆየ:: ለብዙ ሳምንታት ትኩሳቱ አልበረደለትም::አንዳንዴም ያቃዠዋል:: የአያቱ የመሴይ ጊልኖርማንድም ሁኔታ ከማሪየስ
የተለየ አልነበረም:: የልጁ ጉዳይ እስኪለይ ድረስ እርሳቸውም ከአልጋው አጠገብ እየተቀመጡ በሞትና በሽረት መካከል ኖሩ::
በየቀኑ አንዳንዴም በቀን ሁለት ጊዜ አንድ ሽበት የወረረው አዛውንት እየመጣ ይጠይቀዋል:: የሰውየው አለባበስ በጣም ሸጋ ሲሆን ከማረየስ ቤት በመጣ ቁጥር አንድ ነገር ይዞ ነው የሚመጣው::
በመጨረሻ ልክ በታመመ በሦስት ወሩ የማሪየስ በሽታ የማያሰጋ
ለመሆኑ በሐኪሙ ተገለጸ ፤ አያቱ ፈነጠዘ፡፡ ወደ ላይና ወደ ታች ሮጠ፡፡በዚሁ የተነሣ አንድ ቀን ለጎረቤታቸው የደስታ መግለጫ በመላካቸው ሰው ሁሉ ተገረመ:: ሌላው ቀርቶ ማሪየስን «ጌታው» እያለ ይጠሩት ጀመር፡፡
ከነአካቴው ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር» ብሉ እስከመጮህ ደረሱ፡፡ በአጭሩ ጮቤ መቱ።
በማሪየስ በኩል የነበረው አሳብ አንድ ነበር፡፡ ሲያክሙት፣ ቁስሉን
ሲጠግነት፣ እህል ሲቀርብለት፣ አዲስ ሰው ብቅ ሲልም ሆነ በማንኛውም ሰዓት ትዝ የምትለውና እረፍት የምትነሳው ኮዜት ነበረች፡፡ ለእርሱ ሕይወትና ኮዜት አንድ ናቸው:: ኮዜት ከሌለች ሕይወት የለችም:: ከሁለት
አንደኛቸው ከሌሉ ሁለቱም እንደሌሉ በልቡ ወስኖአል::
ማሪየስ ነፍስ ከዘራ በኋላ አንድም ቀን ቢሆን «አባባ» ብሎ ስላልጠራቸው መሴይ ጊልኖርማንድ ይታዘባሉ፡፡ ነገር ግን ጤናው በጣም ተመልሶአል::
አንድ ቀን ከአልጋው ላይ ቁጭ እንዳለ አያቱ ላይ ያፈጥጣል፡፡ ሁለቱ ተያዩ፡፡ ንግግር የሚጀምር ግን ጠፋ:: በመጨረሻ ማሪየስ ዝምታውን ይሰብራል፡፡
‹‹የምነግርህ ነገር ነበረኝ::>
«ምንድነው እሱ?»
«ትዳር ለመያዝ እፈልጋለሁ::»
«ጠርጥሬአለሁ» አሉ አያቱ:: ከዚያም ከት ብለው ሳቁ::
«እንዴት ጠረጠርክ?»
ቀደም ሲል አውቄዋለሁ ፤ አታመልጥህም ታገባታለህ::
ማሪየስ በደስታ ፈነደቀ፡፡ ፊቱ እንደ ማታ ጀምበር እዩኝ እዩኝ አለ::"
እንደ ጠዋት ፀሐይም በራ:: ልቡ እንደ ከበሮ ራሱን ሲደልቅ በውጭ
አልታየም እንጂ በኃይል ተማታ::
አያቱ ንግግራቸውን ቀጠሉ::
«አዎን፣ ያቺ ለግላጋ ፣ ያቺ ሽንኩርት የመሰለች ቆንጆ ያንተው
ትሆናለች:: እንደ አሮጊት ለብሳ ሁናቴህን ለመጠየቅ በየቀኑ ትመላለሳለች።ቆስለህ ከተመለስክ ጀምሮ በየቀኑ እየመጣች አልቅሳ ነው የምትመለሰው::ማን እንደሆነች አጠያያቄ ደርሼበታለሁ:: አድራሻዋንም አወቅሁት፡፡ ለማንኛውም እኛ ተዘጋጅተናል፤ አንተም ፈልገሃል:: እርስዋም ሳትፈልግ አትቀርም፡፡
ስለዚህ ከዚህ በኋላ የቀረው አንድ ነገር ነው! ትዳር መመሥረት፡፡ ነገሩን ስታነሳብኝ እየፈራህ ነው የተናገርከው፡፡ የምጮህብህና የምቆጣህ መስሎህ ነው! አይፈረድብህም:: የለም! አልቆጣም፡፡ ኮዜት ትሁን ወይም ሌላ ፍቅር ብቻ ይስፈን፡፡ አግብተሃት ደስ ብሎህ ኑር ልጄ፡፡»
ሽማግሌው ይህን እንዳሉ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ። እያለቀሱ የማሪየስን ፀጉር አሻሹ፡፡ በዛለ የሽማግሌ እጃቸው አቀፉት፡፡ የደስታ ብዛት መጨረሻው
ለቅሶ ነውና ሁለቱም ለረጅም ጊዜ ተላቀሱ::
‹‹አባባ» አለ ማሪየስ፡፡
«እንግዲያውማ አልጠላኸኝም ማለት ነዋ!» አሉ አያቱ፡፡
ተቃቅፈው ስለቀሩ መነጋገር አልቻሉም:: ቆይተው፣ ቆይተው ግን ሽማግሌው ተናገሩ፡፡
«በል ና፤ ጋሬጣው ተገልጧል፡፡»
ማሪየስ ከተሸሸገበት ከአያቱ ጉያ ብቅ አለ፡፡
«እንግዲያውስ አባባ ሄጄ ልያት፤ አሁን ተሽሎኛል::»
«ይህንንም ጠርጥሬአለሁ፤ ነገ ሄደህ ታያታለህ፡፡»
«አባባ!»
«ምነው?»
«ለምን ዛሬ አይሆንም?»
የሚከለክለን የለም፧ ይህንንም ጠርጥሬአለሀ:::»
ኮዜትና ማሪየስ እንደገና ተገናኙ፡፡ ሲገናኙ ምን እንደተጠያየቁ
ለመግለጸ አንሞክርም:: አንዳንድ ጊዜ አንባቢ ተመራምሮ ማወቅ ያለበትን በመዘርዘር ከሰው ሥራ ወስጥ አንገባም:: እናንተው አስቡት::
በእለቱ ኮዜት ማሪየስን ለመጠየቅ ስትመጣ የቤት ሰው በሙሉ
አንድም ሳይቀር ከማሪየስ ክፍል ይጠብቃታል:: ልክ እርስዋ ከክፍሉ ውስጥ ልትገባ ስትል ሽማግሌ ሊያስነጥሳቸው ይላል፡፡ በመሃረባቸው አፋቸውን
እፍን አደረጉ::
«አይ ቁንጅና!» ይላሉ እርስ በራሳቸው ሲነጋገሩ::
ውስጣዊ ደስታ ፊትን እንደ ብርሃን እንዲበራ ያደርጋል ቢባል የኮዜት
ፊት ማስረጃ ይሆናል:: ኮዜት በደስታ ብዛት ቆነጀች:: ተቅበጠበጠች፣ ሰከረች፣ ዘልላ ሄዳ ከማሪየስ አንገት ላይ ብትጠመጠም ደስ ይላታል፡፡ ግን
ሰው እያለ ፍቅርዋን አደባባይ ማውጣቱ አሳፈራት፡፡ አንዳንድ ጊዜ በፍቅረኞች ላይ እንጨክናለን፡፡ እነርሱ ብቻቸውን መሆን ሲፈልጉ እኛ የሙጥኝ
በማለት አብረን እንቀመጣለን፡፡ እኛ እንፈልጋቸዋለን፤ እነርሱ ግን
አይፈልጉንም
ከኮዜት ጋር አብሮ የመጣ ሰው ነበር፡፡ ይህ ሰው አባባ ሸበቶ ነው::
ይህ ሰው መሴይ ማንደላይን ነው:: ይህ ሰው መሴይ ፎሽለማ ነው፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ዣን ቫልዣ ፊቱን በፈገግታ አስውቦና እሱነቱን በሽበት አስከብሮ ኮዜትን በመከተል ነበር ከቤቱ የገባው:: ሽክ ብሎ ለብሷል፡፡ጥቁር ሱፍ ለብሶ ነጭ ከረቫት አስሮአል::
ሰኔ 6 ቀን እንደዚያ ተጎሳቁሎና ቆሽሾ ማሪየስን ተሸክሞ የመጣው
ሰው ለመሆኑ ሠራተኛው አልጠረጠረም:: ጌታ የጌታ ልጅ መስሎታል ዣን ቫልዣ የተቀመጠው ከበር አጠገብ ሲሆን ከብብቱ ስር እንደ
መጽሐፍ ያለ የተጠቀለለ ነገር ይዟል፡፡ ይህን ያየች የማሪየስ አክስት ወደ አባትዋ ተጠግታ አንድ ነገር ትናገራለች::
«ይህ ሰው ዘወትር መጽሐፍ ይሸከማል?»
መጽሐፍ የሚባል ነገር ጠላትዋ ነው::
«ምን ያድርገው ብለሽ፤ ምሑር እኮ ነው፤ ጥፋት የለበትም» ሲሉ
የማሪየስ አያት መለሰላት::
«መሴይ ፍችለሹ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ::
ስሙን አሳስተው የጠሩት ሽማግሌው ሆን ብለው አልነበረም:: እንደ እርሳቸው የለመዱት የመኳንንት ስሞችን እንጂ እንደ «ፎሽለማ» ያለ ደረሰ
ያልታወቀ ዘር ስም አስተካክሎ መጥራት አይሆንላቸውም::
«መሴይ ፍችለሽ፣ ልጅህን ለልጄ እንድትሰጠኝ እለምናለሁ::»
መሴይ ፎሽለማ ጎንበስ ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ «ተስማምቻለሁ» አለ፡፡
«ተጫወቱ» ብለው ሽማግሌዎቹ ከክፍሉ ውስጥ ጥለዋቸው ወጡ፡፡ኮዜትና ማሪየስ አንገት ለአንገት ለመተቃቀፍ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡
ንግግር አላስፈለጋቸውም:: መተያየትና መታሻሸቱ በቂ ነበር፡፡
መሴይ ጊልኖርማንድ ልጅትዋን በማድነቅ አወሱ፡፡ ስለውበትዋና
ስለቁንጅናዋ ብዙ ተናገሩ:: ፍቅራቸው የፀና እንዲሆንና እርስ በርስ እንዲከባበሩ መከሩ:: ፍቅር ሰዎች ቂል የሚሆኑበትና የእግዚአብሔር ጥበብ የሚገለጽበት ነገር እንደሆነ አስረዱ፡፡
«ብቻ» አሉ ቀጥለው ሊናገሩ፧ «ብቻ እኔ በሕይወት እስካለሁ ድረስ በቂ መተዳዳሪያ ይኖራችኋል፡፡ ከዚያ በኋላ ግን እንጃ! ትቸገራላችሁ፡፡
አሁን በኋላ ፈጣሪ የሀያ ዓመት እድሜ ቢለግሰኝ እንኳን ያለው ንብረት ይበቃል::
«አይጨነቁ፤ ኮዜት ስድስት መቶ ሺህ ፍራንክ አላት::
የዣን ቫልዣ ድምፅ ነበር፡፡
«እኔ!» ስትል ኮዜት ጮኸች::
«ስድስት መቶ ሺህ ፍራንክ?» ሲሉ መሴይ ጊልኖርማንድ ጠየቁ፡፡
«አዎን፤ ስድስት መቶ ሺህ.… ብቻ ምናልባት አሥራ አራት ወይም
አሥራ አምስት ሺህ ፍራንክ ቢቀነስ ነው» ሲል ዣን ቫልዣ ተናገረ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
የልጅ ልጅና አያቱ
ማሪየስ ለረጅም ጊዜ ስለታመመ መሞቱ ወይም በሕይወት መኖሩ
ሳይታወቅ ለረጅም ጊዜ ቆየ:: ለብዙ ሳምንታት ትኩሳቱ አልበረደለትም::አንዳንዴም ያቃዠዋል:: የአያቱ የመሴይ ጊልኖርማንድም ሁኔታ ከማሪየስ
የተለየ አልነበረም:: የልጁ ጉዳይ እስኪለይ ድረስ እርሳቸውም ከአልጋው አጠገብ እየተቀመጡ በሞትና በሽረት መካከል ኖሩ::
በየቀኑ አንዳንዴም በቀን ሁለት ጊዜ አንድ ሽበት የወረረው አዛውንት እየመጣ ይጠይቀዋል:: የሰውየው አለባበስ በጣም ሸጋ ሲሆን ከማረየስ ቤት በመጣ ቁጥር አንድ ነገር ይዞ ነው የሚመጣው::
በመጨረሻ ልክ በታመመ በሦስት ወሩ የማሪየስ በሽታ የማያሰጋ
ለመሆኑ በሐኪሙ ተገለጸ ፤ አያቱ ፈነጠዘ፡፡ ወደ ላይና ወደ ታች ሮጠ፡፡በዚሁ የተነሣ አንድ ቀን ለጎረቤታቸው የደስታ መግለጫ በመላካቸው ሰው ሁሉ ተገረመ:: ሌላው ቀርቶ ማሪየስን «ጌታው» እያለ ይጠሩት ጀመር፡፡
ከነአካቴው ሪፑብሊኩ ለዘላለም ይኑር» ብሉ እስከመጮህ ደረሱ፡፡ በአጭሩ ጮቤ መቱ።
በማሪየስ በኩል የነበረው አሳብ አንድ ነበር፡፡ ሲያክሙት፣ ቁስሉን
ሲጠግነት፣ እህል ሲቀርብለት፣ አዲስ ሰው ብቅ ሲልም ሆነ በማንኛውም ሰዓት ትዝ የምትለውና እረፍት የምትነሳው ኮዜት ነበረች፡፡ ለእርሱ ሕይወትና ኮዜት አንድ ናቸው:: ኮዜት ከሌለች ሕይወት የለችም:: ከሁለት
አንደኛቸው ከሌሉ ሁለቱም እንደሌሉ በልቡ ወስኖአል::
ማሪየስ ነፍስ ከዘራ በኋላ አንድም ቀን ቢሆን «አባባ» ብሎ ስላልጠራቸው መሴይ ጊልኖርማንድ ይታዘባሉ፡፡ ነገር ግን ጤናው በጣም ተመልሶአል::
አንድ ቀን ከአልጋው ላይ ቁጭ እንዳለ አያቱ ላይ ያፈጥጣል፡፡ ሁለቱ ተያዩ፡፡ ንግግር የሚጀምር ግን ጠፋ:: በመጨረሻ ማሪየስ ዝምታውን ይሰብራል፡፡
‹‹የምነግርህ ነገር ነበረኝ::>
«ምንድነው እሱ?»
«ትዳር ለመያዝ እፈልጋለሁ::»
«ጠርጥሬአለሁ» አሉ አያቱ:: ከዚያም ከት ብለው ሳቁ::
«እንዴት ጠረጠርክ?»
ቀደም ሲል አውቄዋለሁ ፤ አታመልጥህም ታገባታለህ::
ማሪየስ በደስታ ፈነደቀ፡፡ ፊቱ እንደ ማታ ጀምበር እዩኝ እዩኝ አለ::"
እንደ ጠዋት ፀሐይም በራ:: ልቡ እንደ ከበሮ ራሱን ሲደልቅ በውጭ
አልታየም እንጂ በኃይል ተማታ::
አያቱ ንግግራቸውን ቀጠሉ::
«አዎን፣ ያቺ ለግላጋ ፣ ያቺ ሽንኩርት የመሰለች ቆንጆ ያንተው
ትሆናለች:: እንደ አሮጊት ለብሳ ሁናቴህን ለመጠየቅ በየቀኑ ትመላለሳለች።ቆስለህ ከተመለስክ ጀምሮ በየቀኑ እየመጣች አልቅሳ ነው የምትመለሰው::ማን እንደሆነች አጠያያቄ ደርሼበታለሁ:: አድራሻዋንም አወቅሁት፡፡ ለማንኛውም እኛ ተዘጋጅተናል፤ አንተም ፈልገሃል:: እርስዋም ሳትፈልግ አትቀርም፡፡
ስለዚህ ከዚህ በኋላ የቀረው አንድ ነገር ነው! ትዳር መመሥረት፡፡ ነገሩን ስታነሳብኝ እየፈራህ ነው የተናገርከው፡፡ የምጮህብህና የምቆጣህ መስሎህ ነው! አይፈረድብህም:: የለም! አልቆጣም፡፡ ኮዜት ትሁን ወይም ሌላ ፍቅር ብቻ ይስፈን፡፡ አግብተሃት ደስ ብሎህ ኑር ልጄ፡፡»
ሽማግሌው ይህን እንዳሉ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ። እያለቀሱ የማሪየስን ፀጉር አሻሹ፡፡ በዛለ የሽማግሌ እጃቸው አቀፉት፡፡ የደስታ ብዛት መጨረሻው
ለቅሶ ነውና ሁለቱም ለረጅም ጊዜ ተላቀሱ::
‹‹አባባ» አለ ማሪየስ፡፡
«እንግዲያውማ አልጠላኸኝም ማለት ነዋ!» አሉ አያቱ፡፡
ተቃቅፈው ስለቀሩ መነጋገር አልቻሉም:: ቆይተው፣ ቆይተው ግን ሽማግሌው ተናገሩ፡፡
«በል ና፤ ጋሬጣው ተገልጧል፡፡»
ማሪየስ ከተሸሸገበት ከአያቱ ጉያ ብቅ አለ፡፡
«እንግዲያውስ አባባ ሄጄ ልያት፤ አሁን ተሽሎኛል::»
«ይህንንም ጠርጥሬአለሁ፤ ነገ ሄደህ ታያታለህ፡፡»
«አባባ!»
«ምነው?»
«ለምን ዛሬ አይሆንም?»
የሚከለክለን የለም፧ ይህንንም ጠርጥሬአለሀ:::»
ኮዜትና ማሪየስ እንደገና ተገናኙ፡፡ ሲገናኙ ምን እንደተጠያየቁ
ለመግለጸ አንሞክርም:: አንዳንድ ጊዜ አንባቢ ተመራምሮ ማወቅ ያለበትን በመዘርዘር ከሰው ሥራ ወስጥ አንገባም:: እናንተው አስቡት::
በእለቱ ኮዜት ማሪየስን ለመጠየቅ ስትመጣ የቤት ሰው በሙሉ
አንድም ሳይቀር ከማሪየስ ክፍል ይጠብቃታል:: ልክ እርስዋ ከክፍሉ ውስጥ ልትገባ ስትል ሽማግሌ ሊያስነጥሳቸው ይላል፡፡ በመሃረባቸው አፋቸውን
እፍን አደረጉ::
«አይ ቁንጅና!» ይላሉ እርስ በራሳቸው ሲነጋገሩ::
ውስጣዊ ደስታ ፊትን እንደ ብርሃን እንዲበራ ያደርጋል ቢባል የኮዜት
ፊት ማስረጃ ይሆናል:: ኮዜት በደስታ ብዛት ቆነጀች:: ተቅበጠበጠች፣ ሰከረች፣ ዘልላ ሄዳ ከማሪየስ አንገት ላይ ብትጠመጠም ደስ ይላታል፡፡ ግን
ሰው እያለ ፍቅርዋን አደባባይ ማውጣቱ አሳፈራት፡፡ አንዳንድ ጊዜ በፍቅረኞች ላይ እንጨክናለን፡፡ እነርሱ ብቻቸውን መሆን ሲፈልጉ እኛ የሙጥኝ
በማለት አብረን እንቀመጣለን፡፡ እኛ እንፈልጋቸዋለን፤ እነርሱ ግን
አይፈልጉንም
ከኮዜት ጋር አብሮ የመጣ ሰው ነበር፡፡ ይህ ሰው አባባ ሸበቶ ነው::
ይህ ሰው መሴይ ማንደላይን ነው:: ይህ ሰው መሴይ ፎሽለማ ነው፡፡ ይህ ሰው ዣን ቫልዣ ነው:: ዣን ቫልዣ ፊቱን በፈገግታ አስውቦና እሱነቱን በሽበት አስከብሮ ኮዜትን በመከተል ነበር ከቤቱ የገባው:: ሽክ ብሎ ለብሷል፡፡ጥቁር ሱፍ ለብሶ ነጭ ከረቫት አስሮአል::
ሰኔ 6 ቀን እንደዚያ ተጎሳቁሎና ቆሽሾ ማሪየስን ተሸክሞ የመጣው
ሰው ለመሆኑ ሠራተኛው አልጠረጠረም:: ጌታ የጌታ ልጅ መስሎታል ዣን ቫልዣ የተቀመጠው ከበር አጠገብ ሲሆን ከብብቱ ስር እንደ
መጽሐፍ ያለ የተጠቀለለ ነገር ይዟል፡፡ ይህን ያየች የማሪየስ አክስት ወደ አባትዋ ተጠግታ አንድ ነገር ትናገራለች::
«ይህ ሰው ዘወትር መጽሐፍ ይሸከማል?»
መጽሐፍ የሚባል ነገር ጠላትዋ ነው::
«ምን ያድርገው ብለሽ፤ ምሑር እኮ ነው፤ ጥፋት የለበትም» ሲሉ
የማሪየስ አያት መለሰላት::
«መሴይ ፍችለሹ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ::
ስሙን አሳስተው የጠሩት ሽማግሌው ሆን ብለው አልነበረም:: እንደ እርሳቸው የለመዱት የመኳንንት ስሞችን እንጂ እንደ «ፎሽለማ» ያለ ደረሰ
ያልታወቀ ዘር ስም አስተካክሎ መጥራት አይሆንላቸውም::
«መሴይ ፍችለሽ፣ ልጅህን ለልጄ እንድትሰጠኝ እለምናለሁ::»
መሴይ ፎሽለማ ጎንበስ ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ «ተስማምቻለሁ» አለ፡፡
«ተጫወቱ» ብለው ሽማግሌዎቹ ከክፍሉ ውስጥ ጥለዋቸው ወጡ፡፡ኮዜትና ማሪየስ አንገት ለአንገት ለመተቃቀፍ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡
ንግግር አላስፈለጋቸውም:: መተያየትና መታሻሸቱ በቂ ነበር፡፡
መሴይ ጊልኖርማንድ ልጅትዋን በማድነቅ አወሱ፡፡ ስለውበትዋና
ስለቁንጅናዋ ብዙ ተናገሩ:: ፍቅራቸው የፀና እንዲሆንና እርስ በርስ እንዲከባበሩ መከሩ:: ፍቅር ሰዎች ቂል የሚሆኑበትና የእግዚአብሔር ጥበብ የሚገለጽበት ነገር እንደሆነ አስረዱ፡፡
«ብቻ» አሉ ቀጥለው ሊናገሩ፧ «ብቻ እኔ በሕይወት እስካለሁ ድረስ በቂ መተዳዳሪያ ይኖራችኋል፡፡ ከዚያ በኋላ ግን እንጃ! ትቸገራላችሁ፡፡
አሁን በኋላ ፈጣሪ የሀያ ዓመት እድሜ ቢለግሰኝ እንኳን ያለው ንብረት ይበቃል::
«አይጨነቁ፤ ኮዜት ስድስት መቶ ሺህ ፍራንክ አላት::
የዣን ቫልዣ ድምፅ ነበር፡፡
«እኔ!» ስትል ኮዜት ጮኸች::
«ስድስት መቶ ሺህ ፍራንክ?» ሲሉ መሴይ ጊልኖርማንድ ጠየቁ፡፡
«አዎን፤ ስድስት መቶ ሺህ.… ብቻ ምናልባት አሥራ አራት ወይም
አሥራ አምስት ሺህ ፍራንክ ቢቀነስ ነው» ሲል ዣን ቫልዣ ተናገረ፡፡
👍19❤2
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....በእራት ሰዓት ግን ዣን ቫልዣ ከሠርጉ ቤት አልነበረም፡፡ ትንሽ
ስላመመው በጊዜ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ የእርሱ ከዚያ አለመገኘት ኮዜትን ቅር አሰኛት:: ሆኖም የእርሱን ቦታ ማሪየስ በመውሰዱ ሀዘንዋ እየተቃለለ ሄደ፡፡ በመጨረሻ ዣን ቫልዣን እስከ መርሳት ደረሰች::...
ዣን ቫልዣ ከቤቱ ሲደርስ ቤቱ ውስጥ ማንም አልነበረም፡፡ ወደ
ኮዜት ክፍል ሲሄድ አልጋዋ አለመነጠፉን ተገነዘበ፡፡ አንሶላዎቹና የትራስ ልብሶች ተነስተዋል፡፡ አንዳንድ የኮዜት የግል እቃዎችም ከዚያ ተወስደዋል፡፡ከዚያ የቀሩት ከባድ የቤት እቃና አራቱ ግድግዳዎች ብቻ ናቸው፡፡ ዣን ቫልዣ ክፍት የነበረውን ሣጥን ዘጋግቶ ከክፍሉ ወጣ፡፡ ክፍሎቹን ሁሉ እየተዘዋወረ ጎበኘ፡፡ ከራሱ መኝታ ቤት ደረሰ፡፡ ወደ አልጋው ሲሄድ ዓይኑ
ከአንድ ነገር ላይ አረፈ፡፡ ዘወትር ከዓይኑ የማይለየው አነስተኛ ሣጥን ከዚያ ተቀምጧል፡፡ ከአጠገቡ ስለማይለየውና በጣም ስለሚንከባከበው ኮዜት
ትቀናበት ነበር፡፡ ከኪሱ ቁልፍ አውጥቶ ትንሹን ሻንጣ ከፈተው::
ከውስጡ የነበሩትን ልብሶች አወጣ፡፡ በመጀመሪያ ጥቁር ቀሚስ፤ ቀጥሎ ጥቁር እስካርፍ፤ ከዚያም ዛሬም ቢሆን ኮዜት ልታደርገው የምትችል ትልቅ የልጅ ጫማ፤ በመጨረሻ ባለኪስ ሽርጥና የተቀደደ የእግር ሹራቦችን
አወጣ፡፡ ኮዜት ከአሥር ዓመት በፊት ሞንትፌርሜን ለቅቃ ስትወጣ የተቀመጠና እናትዋ ከሞተች በኋላ ኮዜትን ፍለጋ ሲሄድ ዣን ቫልዣ የወሰደላት ጥቁር ልብሶች ናቸው:: ልብሶቹን ከአልጋው ላይ ዘርግቶ
እንዳስቀመጣቸው የኮዜት እናት ትዝ አለችው:: በዚያን ጊዜ ኮዜትም ምን ትመስል እንደነበረና እንዴት ከእዚያ አስከፊ ቤት አስወጥቶ ለእናትዋ ሀዘን
ያመጣላትን ጥቁር ልብስ ለብሳ ምን ትመስል እንደነበረ አስታወሰ፡፡ በእናትዋ ሞት ምክንያት ከል ለብሳ እናትዋ በመንፈስ ስታያት ሳትደሰት አልቀረችም ሲል አሰበ፡፡
ኮዜት ከዣን ቫልዣ ጋር ጥቅጥቅ ባለው ጨለማ ያቋረጠችውንም
ጫካ አስታወሰ፡፡ ኮዜት ደስ ብሎአት ያንን የገዛላትን ትልቅ አሻንጉሊት ተሸክማና የሀዘን ልብስ ለብሳ ከማታውቀው ሰው ጋር በደስታ ስትጓዝ ምን ትመስል እንደነበር ትዝ አለው:: ሆዱን ባር ባር አለው፡፡ ከአልጋው ላይ
ከዘረጋው የኮዜት ልብስ ላይ ተደፍቶ ማልቀስ ጀመረ::
ያን እለት ማታ የሕይወቱን የመጨረሻ ትግል፣ የመጨረሻ ፈተና እንደሆነ ዣን ቫልዣ ተገነዘበ፡፡ እንደ ልማዱ ዣን ቫልዣ ከሌላ ፈተና ውስጥ ገባ፡፡
እንዴት አድርጎ ነው የማሪየስንና የኮዜትን ፍቅር ሳያበላሽ አብሮ
የሚኖረው? ለግል ጥቅሙ ሲል ደንቃራ ይሁን ወይስ ብቻውን ውስጥ ውስጡን ይሰቃይ? ይህ ሁልጊዜም ቤተሰቦችን ያስጨነቀና የብዙ ፍቅረኞችን ሕይወት ያበላሸ ጥያቄ ነው::
በሥጋ ፈቃድ ተመርቶ እርምጃ መውሰድ ውጤቱ ግጭት ነው::
ታዲያ እስከመቼ ነው የነፍስ ተገኝዎች ሆነን የምንቀረው? ዣን ቫልዣ ለሥጋው አድሮ ኮዜትን አልለቅም ይበል ወይስ ለነፍሱ አድሮ ሙሉ በሙሉ ለማሪየስ አሳልፎ ይስጣት?
ግን እኮ ቀላል አይደለም:: እርሱስ ምን ይሁን? ከትቢያ አንስቶ ለዚህ
አደረሳት:: የመንፈስ ልጁ ናት:: በዓለም ላይ ያለ እርስዋ ሌላ ሀብት የለውም:: ወንድሙም፣ እህቱም፣ እናቱም፣ አባቱም፣ ጎረቤቱም፣ ምኑም ምኑም ኮዜት ናት:: ኮዜት ትሂድና ሙልጭ ይውጣ? ታዲያ ምን ይሁን?
ታዲያ ለዣን ቫልዣ ሲባል የኮዚት ሕይወት ይበላሽ?
እንዴ፣ ሕይወትዋ የማን ሆነና?
መስዋዕትነት መትነን ነው፣ ለመደሰት መሰቃየት አለ፤ ይህን መፈጸም ማለት ደግሞ ከጋለ ብረት ላይ መቀመጥ ነው:: ግን ካጋለ ብረት ላይ መቀመጥ ከቻለ ዓለምን ከቁጥጥር ስር ማድረግ ይሆናላ!
ዣን ቫልዣ ፍልስፍናውን ትቶ ተስፋ በመቁረጥ ጋደም አለ፡፡ ነገሩን
ሁሉ ለካው፣ መዘነው:: ከዉሳኔ አሳብ ላይ ደረሰ፡፡ እርሱና ጨለማ
ብቻቸውን ቀሩ፡፡
በሠርግ ማግሥት ሁሉም ነገር ጭር ይላል:: ለፍቅረኞች እድል
ለመስጠት ታስቦ ይመስል ሁሉም አርፍዶ ነው ከመኝታው የሚነሳው::ዣን ቫልዣ ግን በጠዋት ተነስቶ ወደ ማሪየስና ኮዜት ቤት ሄደ::
«እርስዎ ነዎት አባባ!» አለ ማሪየስ ዣን ቫልዣ ከነበረበት መጥቶ::
ማሪየስ ብዙም ስላልተኛ በጣም ከብዶታል፡፡
«ምነው በጠዋቱ? ኮዜት ገና አልተነሳችም፡፡ ማታ ቶሎ በመሄድዎ በጣም ቅር አለን፡፡ ስለእርስዎ ብዙ ተጫወትን፡፡ ኮዜት በጣም ትወድዎታለች:
ከዚሁ ጥሩ ክፍል እንደተዘጋጀልዎት ቀደም ብዩ ነግራዎት ነበር፡፡ ከእኛ ጋር መቀመጥ አለብዎት:: ከዚያ ብቻዎን ምን ያደርጋለ? እንዲያውም ከዛሬ ጀምሮ ከዚሁ ነው የሚሆነት:: አባባንም እንደሆነ በመንፈስ ገዝተወታል፡፡ እርሱ የእርስዎ ነገር አይሆንለትም:: በጣም ነው
የሚያከብርዎትና የሚወድዎት፡፡ አብረን የኖርን ተደስተን ነው የምንኖረው።
እርስዎ ደግሞ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ነው የምንፈልገው:: አሁን እንሂድ ቁርስ ቀርቦአል» አለ፡፡
«ሰማሀ ማሪየስ» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «አንድ የምነግርህ ነገር አለ፡፡ እኔ
እንደሆንኩ አሮጌና ሽማግሌ ወንጀለኛ ነኝ::»
አንዳንድ ጊዜ ጆሮ ለመስማት የማይፈልገውን አይሰማም፡፡ በተለይም ካልተጠበቀ ምንጭ የሚወጣ የማይሆን ወሬ ጆሮ ያልፈዋል፡፡ “ወንጀለኛ ነኝ" የሚለውን ዜና ከ መሴይ ፎሽለማ የሚጠበቅ ስላልሆነ የማሪየስ ጆሮ ሊሰማው አልፈቀደም አንድ ነገር ግን እንደሰማ ስለሚያውቅ ፈዝዞ ቀረ።
ምን ማለትዎ ነው?» ሲል በማጉረምረም ይጠይቃል፡፡
«ይህም ማለት» አለ ዣን ቫልዣ ፣ «ወህኒ ቤት ነበርኩ ማለት ነው፡፡»
ምነው እኔን ለማሞኘት ነው?» ሲል ማሪየስ ቅሬታውን ገለጸ፡፡
«ማሪየስ» አለ ዣን ቫልዣ፣ «ከወህኒ ቤት አሥራ ዘጠኝ ዓመት
ኖሬአለሁ:: በሌብነት ወንጀል ተከስሼ ነው የታሰርኩት:: በመጨረሻ ላደረስኩት ጥፋት የእድሜ ልክ እሥራት ተፈርዶብኝ ነበር፡፡ ሆኖም አምልጬ
በመውጣቴ አሁንም ወንጀለኛ ነኝ::
ማሪየስ አሁን መከራከሩ ዋጋ እንደሌለው ስላመነ ዝም ብሎ ይሰማ ጀመር፡፡ ነገሩ እየገባው ሄደ፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው ራሱም ፈራ፡፡
«ይቀጥሉ፤ ይቀጥሉ፤ ሁሉንም ይንገሩኝ» ሲል ተናገረ፡፡ «እርስዎ
የኮዜት አባት ነዎት!»
ፍርሃቱን ለመግለጽ ሁለት እርምጃ ወደኋላ ተራመደ፡፡
ዣን ቫልዣ በኩራት መንፈስ ጭንቅላቱን ወደ ጣራ አቅንቶ ያለምንም ማፈር ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«ምንም እንኳን የምለው ነገር የሚዋጥና የሚጥም ባይሆንም
እንድታምነኝ ያስፈልጋል::)
እዚህ ላይ ዣን ቫልገዥ ጥቂት ቆም ብሎ ንግግሩን በዝግታና ግርማ ሞገስ በተሞላበት አንደበት ቀጠለ፡፡
«ታምነኛለህ ፧ እኔ የኮዜት አባት ነኝ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ግን
አባትዋ አይደለሁም:: ፌቨሮል ከሚባል ሥፍራ ገበሬ ነበርኩ፡፡ ሥራዬ አትክልት መከርከም ነበር:: ስሜ ፎሽለማ ሳይሆን ዣን ቫልዣ ነው:: ከኮዜት ጋር ዝምድና የለንም:: ኣእምርህን ሰብሰብ አድርግ፡፡»
ለማሪየስ እድል ለመስጠት ንግግሩን ካቋረጠ በኋላ እንደገና ጀመረ፡፡
«ታዲያ ለኮዜት ምንዋ ነኝ?አዛኝ! ከአሥር ዓመት በፊት በሕይወት
መኖርዋን እንኳን አላውቅም ነበር፡፡ በእርግጥ እወዳታለሁ፡፡ የሙት ልጅ ስለሆነች አባትና እናት የላትም:: የዛሬ አሥር ዓመት ገደማ የእኔን እርዳታ በጣም ያስፈልጋት ስለነበር እርስዋን ማፍቀር ጀመርኩ፡፡ ልጆች ደካሞች
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ሶስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....በእራት ሰዓት ግን ዣን ቫልዣ ከሠርጉ ቤት አልነበረም፡፡ ትንሽ
ስላመመው በጊዜ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ የእርሱ ከዚያ አለመገኘት ኮዜትን ቅር አሰኛት:: ሆኖም የእርሱን ቦታ ማሪየስ በመውሰዱ ሀዘንዋ እየተቃለለ ሄደ፡፡ በመጨረሻ ዣን ቫልዣን እስከ መርሳት ደረሰች::...
ዣን ቫልዣ ከቤቱ ሲደርስ ቤቱ ውስጥ ማንም አልነበረም፡፡ ወደ
ኮዜት ክፍል ሲሄድ አልጋዋ አለመነጠፉን ተገነዘበ፡፡ አንሶላዎቹና የትራስ ልብሶች ተነስተዋል፡፡ አንዳንድ የኮዜት የግል እቃዎችም ከዚያ ተወስደዋል፡፡ከዚያ የቀሩት ከባድ የቤት እቃና አራቱ ግድግዳዎች ብቻ ናቸው፡፡ ዣን ቫልዣ ክፍት የነበረውን ሣጥን ዘጋግቶ ከክፍሉ ወጣ፡፡ ክፍሎቹን ሁሉ እየተዘዋወረ ጎበኘ፡፡ ከራሱ መኝታ ቤት ደረሰ፡፡ ወደ አልጋው ሲሄድ ዓይኑ
ከአንድ ነገር ላይ አረፈ፡፡ ዘወትር ከዓይኑ የማይለየው አነስተኛ ሣጥን ከዚያ ተቀምጧል፡፡ ከአጠገቡ ስለማይለየውና በጣም ስለሚንከባከበው ኮዜት
ትቀናበት ነበር፡፡ ከኪሱ ቁልፍ አውጥቶ ትንሹን ሻንጣ ከፈተው::
ከውስጡ የነበሩትን ልብሶች አወጣ፡፡ በመጀመሪያ ጥቁር ቀሚስ፤ ቀጥሎ ጥቁር እስካርፍ፤ ከዚያም ዛሬም ቢሆን ኮዜት ልታደርገው የምትችል ትልቅ የልጅ ጫማ፤ በመጨረሻ ባለኪስ ሽርጥና የተቀደደ የእግር ሹራቦችን
አወጣ፡፡ ኮዜት ከአሥር ዓመት በፊት ሞንትፌርሜን ለቅቃ ስትወጣ የተቀመጠና እናትዋ ከሞተች በኋላ ኮዜትን ፍለጋ ሲሄድ ዣን ቫልዣ የወሰደላት ጥቁር ልብሶች ናቸው:: ልብሶቹን ከአልጋው ላይ ዘርግቶ
እንዳስቀመጣቸው የኮዜት እናት ትዝ አለችው:: በዚያን ጊዜ ኮዜትም ምን ትመስል እንደነበረና እንዴት ከእዚያ አስከፊ ቤት አስወጥቶ ለእናትዋ ሀዘን
ያመጣላትን ጥቁር ልብስ ለብሳ ምን ትመስል እንደነበረ አስታወሰ፡፡ በእናትዋ ሞት ምክንያት ከል ለብሳ እናትዋ በመንፈስ ስታያት ሳትደሰት አልቀረችም ሲል አሰበ፡፡
ኮዜት ከዣን ቫልዣ ጋር ጥቅጥቅ ባለው ጨለማ ያቋረጠችውንም
ጫካ አስታወሰ፡፡ ኮዜት ደስ ብሎአት ያንን የገዛላትን ትልቅ አሻንጉሊት ተሸክማና የሀዘን ልብስ ለብሳ ከማታውቀው ሰው ጋር በደስታ ስትጓዝ ምን ትመስል እንደነበር ትዝ አለው:: ሆዱን ባር ባር አለው፡፡ ከአልጋው ላይ
ከዘረጋው የኮዜት ልብስ ላይ ተደፍቶ ማልቀስ ጀመረ::
ያን እለት ማታ የሕይወቱን የመጨረሻ ትግል፣ የመጨረሻ ፈተና እንደሆነ ዣን ቫልዣ ተገነዘበ፡፡ እንደ ልማዱ ዣን ቫልዣ ከሌላ ፈተና ውስጥ ገባ፡፡
እንዴት አድርጎ ነው የማሪየስንና የኮዜትን ፍቅር ሳያበላሽ አብሮ
የሚኖረው? ለግል ጥቅሙ ሲል ደንቃራ ይሁን ወይስ ብቻውን ውስጥ ውስጡን ይሰቃይ? ይህ ሁልጊዜም ቤተሰቦችን ያስጨነቀና የብዙ ፍቅረኞችን ሕይወት ያበላሸ ጥያቄ ነው::
በሥጋ ፈቃድ ተመርቶ እርምጃ መውሰድ ውጤቱ ግጭት ነው::
ታዲያ እስከመቼ ነው የነፍስ ተገኝዎች ሆነን የምንቀረው? ዣን ቫልዣ ለሥጋው አድሮ ኮዜትን አልለቅም ይበል ወይስ ለነፍሱ አድሮ ሙሉ በሙሉ ለማሪየስ አሳልፎ ይስጣት?
ግን እኮ ቀላል አይደለም:: እርሱስ ምን ይሁን? ከትቢያ አንስቶ ለዚህ
አደረሳት:: የመንፈስ ልጁ ናት:: በዓለም ላይ ያለ እርስዋ ሌላ ሀብት የለውም:: ወንድሙም፣ እህቱም፣ እናቱም፣ አባቱም፣ ጎረቤቱም፣ ምኑም ምኑም ኮዜት ናት:: ኮዜት ትሂድና ሙልጭ ይውጣ? ታዲያ ምን ይሁን?
ታዲያ ለዣን ቫልዣ ሲባል የኮዚት ሕይወት ይበላሽ?
እንዴ፣ ሕይወትዋ የማን ሆነና?
መስዋዕትነት መትነን ነው፣ ለመደሰት መሰቃየት አለ፤ ይህን መፈጸም ማለት ደግሞ ከጋለ ብረት ላይ መቀመጥ ነው:: ግን ካጋለ ብረት ላይ መቀመጥ ከቻለ ዓለምን ከቁጥጥር ስር ማድረግ ይሆናላ!
ዣን ቫልዣ ፍልስፍናውን ትቶ ተስፋ በመቁረጥ ጋደም አለ፡፡ ነገሩን
ሁሉ ለካው፣ መዘነው:: ከዉሳኔ አሳብ ላይ ደረሰ፡፡ እርሱና ጨለማ
ብቻቸውን ቀሩ፡፡
በሠርግ ማግሥት ሁሉም ነገር ጭር ይላል:: ለፍቅረኞች እድል
ለመስጠት ታስቦ ይመስል ሁሉም አርፍዶ ነው ከመኝታው የሚነሳው::ዣን ቫልዣ ግን በጠዋት ተነስቶ ወደ ማሪየስና ኮዜት ቤት ሄደ::
«እርስዎ ነዎት አባባ!» አለ ማሪየስ ዣን ቫልዣ ከነበረበት መጥቶ::
ማሪየስ ብዙም ስላልተኛ በጣም ከብዶታል፡፡
«ምነው በጠዋቱ? ኮዜት ገና አልተነሳችም፡፡ ማታ ቶሎ በመሄድዎ በጣም ቅር አለን፡፡ ስለእርስዎ ብዙ ተጫወትን፡፡ ኮዜት በጣም ትወድዎታለች:
ከዚሁ ጥሩ ክፍል እንደተዘጋጀልዎት ቀደም ብዩ ነግራዎት ነበር፡፡ ከእኛ ጋር መቀመጥ አለብዎት:: ከዚያ ብቻዎን ምን ያደርጋለ? እንዲያውም ከዛሬ ጀምሮ ከዚሁ ነው የሚሆነት:: አባባንም እንደሆነ በመንፈስ ገዝተወታል፡፡ እርሱ የእርስዎ ነገር አይሆንለትም:: በጣም ነው
የሚያከብርዎትና የሚወድዎት፡፡ አብረን የኖርን ተደስተን ነው የምንኖረው።
እርስዎ ደግሞ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ነው የምንፈልገው:: አሁን እንሂድ ቁርስ ቀርቦአል» አለ፡፡
«ሰማሀ ማሪየስ» አለ ዣን ቫልዣ ፤ «አንድ የምነግርህ ነገር አለ፡፡ እኔ
እንደሆንኩ አሮጌና ሽማግሌ ወንጀለኛ ነኝ::»
አንዳንድ ጊዜ ጆሮ ለመስማት የማይፈልገውን አይሰማም፡፡ በተለይም ካልተጠበቀ ምንጭ የሚወጣ የማይሆን ወሬ ጆሮ ያልፈዋል፡፡ “ወንጀለኛ ነኝ" የሚለውን ዜና ከ መሴይ ፎሽለማ የሚጠበቅ ስላልሆነ የማሪየስ ጆሮ ሊሰማው አልፈቀደም አንድ ነገር ግን እንደሰማ ስለሚያውቅ ፈዝዞ ቀረ።
ምን ማለትዎ ነው?» ሲል በማጉረምረም ይጠይቃል፡፡
«ይህም ማለት» አለ ዣን ቫልዣ ፣ «ወህኒ ቤት ነበርኩ ማለት ነው፡፡»
ምነው እኔን ለማሞኘት ነው?» ሲል ማሪየስ ቅሬታውን ገለጸ፡፡
«ማሪየስ» አለ ዣን ቫልዣ፣ «ከወህኒ ቤት አሥራ ዘጠኝ ዓመት
ኖሬአለሁ:: በሌብነት ወንጀል ተከስሼ ነው የታሰርኩት:: በመጨረሻ ላደረስኩት ጥፋት የእድሜ ልክ እሥራት ተፈርዶብኝ ነበር፡፡ ሆኖም አምልጬ
በመውጣቴ አሁንም ወንጀለኛ ነኝ::
ማሪየስ አሁን መከራከሩ ዋጋ እንደሌለው ስላመነ ዝም ብሎ ይሰማ ጀመር፡፡ ነገሩ እየገባው ሄደ፡፡ እንዲያውም ከነአካቴው ራሱም ፈራ፡፡
«ይቀጥሉ፤ ይቀጥሉ፤ ሁሉንም ይንገሩኝ» ሲል ተናገረ፡፡ «እርስዎ
የኮዜት አባት ነዎት!»
ፍርሃቱን ለመግለጽ ሁለት እርምጃ ወደኋላ ተራመደ፡፡
ዣን ቫልዣ በኩራት መንፈስ ጭንቅላቱን ወደ ጣራ አቅንቶ ያለምንም ማፈር ንግግሩን ቀጠለ፡፡
«ምንም እንኳን የምለው ነገር የሚዋጥና የሚጥም ባይሆንም
እንድታምነኝ ያስፈልጋል::)
እዚህ ላይ ዣን ቫልገዥ ጥቂት ቆም ብሎ ንግግሩን በዝግታና ግርማ ሞገስ በተሞላበት አንደበት ቀጠለ፡፡
«ታምነኛለህ ፧ እኔ የኮዜት አባት ነኝ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ግን
አባትዋ አይደለሁም:: ፌቨሮል ከሚባል ሥፍራ ገበሬ ነበርኩ፡፡ ሥራዬ አትክልት መከርከም ነበር:: ስሜ ፎሽለማ ሳይሆን ዣን ቫልዣ ነው:: ከኮዜት ጋር ዝምድና የለንም:: ኣእምርህን ሰብሰብ አድርግ፡፡»
ለማሪየስ እድል ለመስጠት ንግግሩን ካቋረጠ በኋላ እንደገና ጀመረ፡፡
«ታዲያ ለኮዜት ምንዋ ነኝ?አዛኝ! ከአሥር ዓመት በፊት በሕይወት
መኖርዋን እንኳን አላውቅም ነበር፡፡ በእርግጥ እወዳታለሁ፡፡ የሙት ልጅ ስለሆነች አባትና እናት የላትም:: የዛሬ አሥር ዓመት ገደማ የእኔን እርዳታ በጣም ያስፈልጋት ስለነበር እርስዋን ማፍቀር ጀመርኩ፡፡ ልጆች ደካሞች
👍19
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ደክሞ የጨለመው ውጋጋን ሲፈካ
በሚቀጥለው ቀን ዣን ቫልዣ ከነኮዜት ቤት ሲሄድ ዘበኛው ትእዛዝ የተሰጠው ይመስል ከበራፍ ቆሞ ጠብቆት ወደ ምድር ቤት ይዞት ሄደ:: ዣን ቫልዣ በጣም ደክሞታል ባለፉት ጥቂት ቀናት እህል አልቀመሰም፤ብዙም እንቅልፍ አልተኛም:
ከጥቂት ጊዜ በኋላ ኮዜት መጥታ ‹ሰላምታ» ስትሰጠው ዞር ብሎ
በማፍጠጥ አያት
‹‹ምነው አባባ፣ ሰሞኑን ደስ አላለህም? ምነው ይህን ጨለማ ቤት መረጥክ! ከዚህ ለመሆን እንደፈለግህ ማሪየስ ነግሮኛል »
«አዎን፣ ነግሬዋለሁ፡፡››
«ትስመኛለህ ብዬ ጉንጬን ሳቀርብ ፊትህን አዞርክብኝሳ? እስቲ አሁን
ሳመኝ:»
እንደመጀመሪያው አሁንም ፊቱን አዞረባት እንጂ አልሳማትም::
«አሁን የከበደው መጣ» አለች ኮዜት እንደመቀለድ ብላ:፡ «ምን አደረግሁ? ግራ ነው የገባኝ፡ ለዚህ ማካካሻ እራት ከእኛ ጋር መብላት አለብህ::››
«በልቼአለሁ:»
«ውሸት ነው፡፡ ና እባክህ፤ አሁኑኑ ወደ ምግብ ቤት እንሂድ»
«አልችልም »
ኮዜት ጨነቃትና በትእዛዝ መልክ ከማናገር ቆጠብ አለች
ለምንግን? እንድንገናኝበት የመረጥከው ክፍል አስቀያሚ ክፍል
ስለሆነ አስጠላህ?»
«ሰማሽ እመቤቴ፧ ታውቂኛለሽ‥ ጠባዬ ከሰው አይገጥምም::›
«እመቤቴ! ይሁና!»
«እመቤቴ መባልን ፈለግሽ: ይኸው አገኘሽው:»
«እመቤትነቴ ለአንተ አይደለማ!»
«ከአሁን በኋላ አባባ እያልሽ ባትጠሪኝ መልካም ነው»
«ምን?»
«መሴይ ዣን ቫልዣ ብለሽ ጥሪኝ፤ ከፈለግሽ ዣንም ይበቃል»
«በቃ ከአሁን በኋላ አባቴ አይደለህም ማለት ነው? እኔም ከአሁን
ወዲያ ልጅህ ኮዜት አይደለሁም ማለት ነው? ይህ ምን ማለት ነው? ምነው
ጠላኸኝ? መከራ ውስጥ ነው የዘፈቅኸኝ:»
በድንገት ኮስተርተር ብላ ዣን ቫልዣ ላይ አፈጠጠችበት:
እያፈጠጠችም የሚከተለውን ቀጥላ ጠየቀችው::
«እኔን ደስ ሲለኝ አትወድም ማለት ነው?»
አንዳንድ ጊዜ አንድ ሰው የአነጋገር ዘይቤ ሳያውቅ ቀርቶ እንዳመጣለት ሲናገር ንግግሩ አጥንት ሰብሮ ይገባል፡ ይህ ጥያቄ ለኮዜት ቀላል ቢመስልም
ለዣን ቫልዣ ከአሜከላ የበለጠ የሚዋጋ ነበር፡ ኮዜት እሰፋለሁ ብላ ተረተረች:: የዣን ቫልዣ ፊት በድንጋጤ አመድ መሰለ፡፡ ለጥቂት ጊዜ ለጥያቄው መልሰ ሳይሰጥ ዝም አለ፡፡ በመጨረሻ በቃላት ሊገልጽ በማይቻል የአነጋገር ስልት በጣም ዝግ ብሎ እርሱ በራሱ ይነጋገር ይመስል
በማጉረምረም ተናገረ::
«የእርስዋ ደስታ የሕይወቴ ግብ ነበር፡ አሁንስ እግዜር ቢወስደኝ ይሻላል፡ ኮዜት ደስ ብሎሻል፡ ከአሁን በኋላ በቃኝ»
«ጎሽ 'ኮዜት ብለህ ነው እኮ የጠራኸኝ: 'እመቤት አላልክም» ስትል ጮኸች:: ዘልላ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመች::
ዣን ቫልዣ የሚያደርገውን ቢያጣ ጭምቅ አድርጎ አቀፋት፡፡ ወደ ቤቱ መልሶ የሚወስዳት መሰለው
«እግዚአብሔር ይስጥልኝ፣ አባዬ» አለችው፡፡
ዣን ቫልዣ ቀስ ብሎ ራሱን ካላቀቀ በኋላ ቆቡን አነሳ፡
«እና!» አለች ኮዜት
«ልሂድ» አለ ዣን ቫልዣ ፧ «ይጠብቁሻል ኮዜት» በሩ አጠገብ ሲደርስ መለስ ብሎ ኮዜት ብዬ ጠራሁሽ እኮ ሁለተኛ እንደማይደገምና ይቅርታም እንደጠየቅሁ ለባልሽ ንገሪው፡፡›
ዣን ቫልዣ ወጥቶ ሄደ ኮዜት ከቆመችበት ፈዝዛ ቀረች በሚቀጥለው ቀን በዚያቹ ሰዓት ዣን ቫልዣ ተመልሶ መጣ: ኮዜት
ግን ነገር አላበዛችበትም: መሴይ ዣን» ወይም «አባባ» ብላ ላለመጥራት
ጥንቃቄ አደረገች የፈለገውን እንዲናገር እድል ሰጠችው፡ ማዘንዋንም ላለማሳየት ሞከረች
ምናልባት ከማሪየስ ጋር ስለ ዣንቫልዣ ተነጋግረ ይሆናል:: ሆኖም የሚወዱት ወንድ ቢቀባጥርና ያፈቀደውን ቢናገር ብልጫና ፍሬ ያለው ንግግር እንደተናገረ በመቁጠር በቀላሉ እንደሚረኩበት ሁሉ ያፈቀረችውም ሴት እንዲሁ በቀላሉ ስለምትታለል እርስ በርስ በመተማመን በንግግራቸው ብዙም አልተጨቃጨቁ ይሆናል የፍቅረኞች የማወቅ ጉጉት ከፍቅራቸው አያልፍምና::
በዚህ ዓይነት ብዙ ሳምንቶች አለፉ ዣን ቫልዣ በየቀኑ እየመጣ ዓይንዋን ብቻ አይቶ ይሄዳል: ኮዜት ግን ሀዘንዋ እየቀለላት መጣ እንጂ
ለዣን ቫል የነበራት ፍቅር አልተቀነሶም ዓይንዋን ማየት ዣን ቫልዣን
ያረካዋል አንድ ቀን እንደለመደው ከነኮዜት ቤት ሲመጣ ኮዜት በመርሳት
«አባባ» ስትል ጠራችው:: እርሱ መልሶ «ዣን ይላታል፡ «ይቅርታ፣
መሴይዣን» ትለዋለች እየሳቀች: «ልክ ነሽ» ብሎ ከመለሰላት በኋላ
እንባው ሲወርድ እንዳታየው ፊቱን ወደ መስኮት አዙሮ እንደመናፈጥ
በማለት እንባውን ይጠራርጋል
ዣን ቫልዣ በመጣ ቁጥር ዘወትር ከሚገባበት ክፍል እሳት ተቀጣጥሎ
ነበር የሚጠብቀው: አንድ ቀን ሲመጣ እሳቱ ሳይቀጣጠል ይቀራል: ቆይቶ
ደግሞ በሌላ ቀን ሲመጣ ይቀመጥበት የነበረው ወንበር ከቦታው ይነሳል
በሌላ ቀን ከክፍሉ ውስጥ ጨርሶ ወንበር አይቀመጥም፡ በዚህ ጊዜ
እንዳልተፈለገ ገባው፡ ኮዜት «ለምን እሳቱ አልተያያዘም? ወንበሮቹስ የት ሄዱ? ብላ ስትጠይቅ ዣን ቫልዣ እኔ አዝዤ ነው» ይላታል በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ከነኮዜት ቤት ሳይመጣ ቀረ፡ ኮዜት ሰው
ከቤቱ ላከች::
‹‹ምነው ትናንት ሳትመጣ ቀረህ?» ብለዋል እመቤቴ
«ከትናንት ወዲያም አልመጣሁም» አለ ሳቅ እያለ ሠራተኛዋ አልገባትም፡ ስትመለስ ከ ዣን ቫልዣ ደኅንነት በስተቀር
ለኮዜት ሌላ ነገር አልነገረቻትም
በ1833 ዓ.ም መጀመሪያ አጋማሽ ፓሪስ ከተማ ውስጥ ማሬይ ከተባለ ቀበሌ አካባቢ የሚኖሩ ባለሱቆችና ቦዘኔዎች አንድ ነገር ያያለዘሉ:: አንድ ከወገቡ የጎበጠ፣ ከፀጉሩ የሸበተ ሽማግሌ በየቀኑ በተወሰነ ሰዓት ሽርሽር ይወጣል:: የሚሄድበት መንገድ አንድ ሆኖ ሳለ የሚሸፍነው ርቀት ግን በየቀኑ በትንሽ በትንሹ ይቀንሳል የሚራመደው በጣም ዝግ ብሉ ሲሆን አንድም ቀን ግራና ቀኝ ሳያይ እንዳቀረቀረ ወደፊት ነው የሚጓዘው
አንድ ከተወሰነ ስፍራ ሲደርስ ፊቱ ወገግ ይልና እርስ በራሱ ብቻውን ያወራል ማውራቱን ለማወቅ የሚቻለው ከንፈሮቹ ሲነቃነቁ ነው: ካልቬር ከተባለ ጎዳና ላይ ከሚገኝ አደባባይ ሲደርስ ቆም ይልና አካባቢውን ይቃኛል
" አካባቢውን ቃኝቶ ከጨረሰ በኋላ በአሳብ ተውጦ ዓይኑ እንባ ያቀርራል:
ጥቂት ካለቀሰ በኋላ በመጣበት መንገድ ይመለሳል
ቀን እያለፈ ሲሄድ አደባባዩን በሩቁ ማየት እንጂ ከእዚያ ለመድረስ አልቻለም፡ ሰውነቱ እየደከመ ሄደ:፡ ወደኋላማ ወደ አደባባዩ መጠምዘዣ መድረስ እንኳን ተሳነው፡፡ በየቀኑ በዚህ ዓይነት በተወሰነ ሰዓት ከቤቱ እየወጣ ጉልበቱ እስከፈቀደለት ድረስ ተጉዞ ይመለሳል፡፡ ዝናብ ሲሆን ጥላ ይይዛል፡ ብርድ ሲሆን ካፖርት ይለብሳል፡ የሚሸፍነው ርቀት ባጠረ ቁጥር ከደረሰበት ቆም ይልና አንገቱን ከነቀነቀ በኋላ ግራ ቀኙን ተመልክቶ ይመለሳል፡፡ ከጊዜ በኋላ የተቀነሰው መንገዱ ብቻ አልነበረም፤ የእንባውም ዘለላ ተቀነሰ፡ በመጨረሻ እስከነአካቴው ዓይኑ ደርቆ ለማልቀስ ቢፈልግም እምባ አይወጣውም:፡ በየእለቱ ሽማግሌው ብቅ ሲል አንዲት አሮጊት «የሚገርም ነው‥ ሰዓቱን ጠብቆ ይመጣል፣ አይቀራትም መቼም» ይላሉ፡
ከተወሰነ ነጥብ ሲደርስ ደግሞ ልጆች እየሳቁ ይከተሉታል
አንድ ቀን ዣን ቫልዣ ከቤቱ ወጥቶ ከዋናው ጎዳና ሲደርስ ሦስት
እርምጃ ወደፊት ከተራመደ በኋላ ከድንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡ ሰኔ 5 ቀን
ከዚህች ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ ነው ጋቭሮችን ያነጋገረው:፡ ጥቂት አወጣ፣
አወረደና ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ከዚያ በኋላ ለሽርሽር መውጣት አልቻለም::
በሚቀጥለው ቀን ከክፍሉም አልወጣም:: አሁንም በሚቀጥለው ቀን ከአልጋው አልተነሳም::
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አራት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ደክሞ የጨለመው ውጋጋን ሲፈካ
በሚቀጥለው ቀን ዣን ቫልዣ ከነኮዜት ቤት ሲሄድ ዘበኛው ትእዛዝ የተሰጠው ይመስል ከበራፍ ቆሞ ጠብቆት ወደ ምድር ቤት ይዞት ሄደ:: ዣን ቫልዣ በጣም ደክሞታል ባለፉት ጥቂት ቀናት እህል አልቀመሰም፤ብዙም እንቅልፍ አልተኛም:
ከጥቂት ጊዜ በኋላ ኮዜት መጥታ ‹ሰላምታ» ስትሰጠው ዞር ብሎ
በማፍጠጥ አያት
‹‹ምነው አባባ፣ ሰሞኑን ደስ አላለህም? ምነው ይህን ጨለማ ቤት መረጥክ! ከዚህ ለመሆን እንደፈለግህ ማሪየስ ነግሮኛል »
«አዎን፣ ነግሬዋለሁ፡፡››
«ትስመኛለህ ብዬ ጉንጬን ሳቀርብ ፊትህን አዞርክብኝሳ? እስቲ አሁን
ሳመኝ:»
እንደመጀመሪያው አሁንም ፊቱን አዞረባት እንጂ አልሳማትም::
«አሁን የከበደው መጣ» አለች ኮዜት እንደመቀለድ ብላ:፡ «ምን አደረግሁ? ግራ ነው የገባኝ፡ ለዚህ ማካካሻ እራት ከእኛ ጋር መብላት አለብህ::››
«በልቼአለሁ:»
«ውሸት ነው፡፡ ና እባክህ፤ አሁኑኑ ወደ ምግብ ቤት እንሂድ»
«አልችልም »
ኮዜት ጨነቃትና በትእዛዝ መልክ ከማናገር ቆጠብ አለች
ለምንግን? እንድንገናኝበት የመረጥከው ክፍል አስቀያሚ ክፍል
ስለሆነ አስጠላህ?»
«ሰማሽ እመቤቴ፧ ታውቂኛለሽ‥ ጠባዬ ከሰው አይገጥምም::›
«እመቤቴ! ይሁና!»
«እመቤቴ መባልን ፈለግሽ: ይኸው አገኘሽው:»
«እመቤትነቴ ለአንተ አይደለማ!»
«ከአሁን በኋላ አባባ እያልሽ ባትጠሪኝ መልካም ነው»
«ምን?»
«መሴይ ዣን ቫልዣ ብለሽ ጥሪኝ፤ ከፈለግሽ ዣንም ይበቃል»
«በቃ ከአሁን በኋላ አባቴ አይደለህም ማለት ነው? እኔም ከአሁን
ወዲያ ልጅህ ኮዜት አይደለሁም ማለት ነው? ይህ ምን ማለት ነው? ምነው
ጠላኸኝ? መከራ ውስጥ ነው የዘፈቅኸኝ:»
በድንገት ኮስተርተር ብላ ዣን ቫልዣ ላይ አፈጠጠችበት:
እያፈጠጠችም የሚከተለውን ቀጥላ ጠየቀችው::
«እኔን ደስ ሲለኝ አትወድም ማለት ነው?»
አንዳንድ ጊዜ አንድ ሰው የአነጋገር ዘይቤ ሳያውቅ ቀርቶ እንዳመጣለት ሲናገር ንግግሩ አጥንት ሰብሮ ይገባል፡ ይህ ጥያቄ ለኮዜት ቀላል ቢመስልም
ለዣን ቫልዣ ከአሜከላ የበለጠ የሚዋጋ ነበር፡ ኮዜት እሰፋለሁ ብላ ተረተረች:: የዣን ቫልዣ ፊት በድንጋጤ አመድ መሰለ፡፡ ለጥቂት ጊዜ ለጥያቄው መልሰ ሳይሰጥ ዝም አለ፡፡ በመጨረሻ በቃላት ሊገልጽ በማይቻል የአነጋገር ስልት በጣም ዝግ ብሎ እርሱ በራሱ ይነጋገር ይመስል
በማጉረምረም ተናገረ::
«የእርስዋ ደስታ የሕይወቴ ግብ ነበር፡ አሁንስ እግዜር ቢወስደኝ ይሻላል፡ ኮዜት ደስ ብሎሻል፡ ከአሁን በኋላ በቃኝ»
«ጎሽ 'ኮዜት ብለህ ነው እኮ የጠራኸኝ: 'እመቤት አላልክም» ስትል ጮኸች:: ዘልላ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመች::
ዣን ቫልዣ የሚያደርገውን ቢያጣ ጭምቅ አድርጎ አቀፋት፡፡ ወደ ቤቱ መልሶ የሚወስዳት መሰለው
«እግዚአብሔር ይስጥልኝ፣ አባዬ» አለችው፡፡
ዣን ቫልዣ ቀስ ብሎ ራሱን ካላቀቀ በኋላ ቆቡን አነሳ፡
«እና!» አለች ኮዜት
«ልሂድ» አለ ዣን ቫልዣ ፧ «ይጠብቁሻል ኮዜት» በሩ አጠገብ ሲደርስ መለስ ብሎ ኮዜት ብዬ ጠራሁሽ እኮ ሁለተኛ እንደማይደገምና ይቅርታም እንደጠየቅሁ ለባልሽ ንገሪው፡፡›
ዣን ቫልዣ ወጥቶ ሄደ ኮዜት ከቆመችበት ፈዝዛ ቀረች በሚቀጥለው ቀን በዚያቹ ሰዓት ዣን ቫልዣ ተመልሶ መጣ: ኮዜት
ግን ነገር አላበዛችበትም: መሴይ ዣን» ወይም «አባባ» ብላ ላለመጥራት
ጥንቃቄ አደረገች የፈለገውን እንዲናገር እድል ሰጠችው፡ ማዘንዋንም ላለማሳየት ሞከረች
ምናልባት ከማሪየስ ጋር ስለ ዣንቫልዣ ተነጋግረ ይሆናል:: ሆኖም የሚወዱት ወንድ ቢቀባጥርና ያፈቀደውን ቢናገር ብልጫና ፍሬ ያለው ንግግር እንደተናገረ በመቁጠር በቀላሉ እንደሚረኩበት ሁሉ ያፈቀረችውም ሴት እንዲሁ በቀላሉ ስለምትታለል እርስ በርስ በመተማመን በንግግራቸው ብዙም አልተጨቃጨቁ ይሆናል የፍቅረኞች የማወቅ ጉጉት ከፍቅራቸው አያልፍምና::
በዚህ ዓይነት ብዙ ሳምንቶች አለፉ ዣን ቫልዣ በየቀኑ እየመጣ ዓይንዋን ብቻ አይቶ ይሄዳል: ኮዜት ግን ሀዘንዋ እየቀለላት መጣ እንጂ
ለዣን ቫል የነበራት ፍቅር አልተቀነሶም ዓይንዋን ማየት ዣን ቫልዣን
ያረካዋል አንድ ቀን እንደለመደው ከነኮዜት ቤት ሲመጣ ኮዜት በመርሳት
«አባባ» ስትል ጠራችው:: እርሱ መልሶ «ዣን ይላታል፡ «ይቅርታ፣
መሴይዣን» ትለዋለች እየሳቀች: «ልክ ነሽ» ብሎ ከመለሰላት በኋላ
እንባው ሲወርድ እንዳታየው ፊቱን ወደ መስኮት አዙሮ እንደመናፈጥ
በማለት እንባውን ይጠራርጋል
ዣን ቫልዣ በመጣ ቁጥር ዘወትር ከሚገባበት ክፍል እሳት ተቀጣጥሎ
ነበር የሚጠብቀው: አንድ ቀን ሲመጣ እሳቱ ሳይቀጣጠል ይቀራል: ቆይቶ
ደግሞ በሌላ ቀን ሲመጣ ይቀመጥበት የነበረው ወንበር ከቦታው ይነሳል
በሌላ ቀን ከክፍሉ ውስጥ ጨርሶ ወንበር አይቀመጥም፡ በዚህ ጊዜ
እንዳልተፈለገ ገባው፡ ኮዜት «ለምን እሳቱ አልተያያዘም? ወንበሮቹስ የት ሄዱ? ብላ ስትጠይቅ ዣን ቫልዣ እኔ አዝዤ ነው» ይላታል በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ከነኮዜት ቤት ሳይመጣ ቀረ፡ ኮዜት ሰው
ከቤቱ ላከች::
‹‹ምነው ትናንት ሳትመጣ ቀረህ?» ብለዋል እመቤቴ
«ከትናንት ወዲያም አልመጣሁም» አለ ሳቅ እያለ ሠራተኛዋ አልገባትም፡ ስትመለስ ከ ዣን ቫልዣ ደኅንነት በስተቀር
ለኮዜት ሌላ ነገር አልነገረቻትም
በ1833 ዓ.ም መጀመሪያ አጋማሽ ፓሪስ ከተማ ውስጥ ማሬይ ከተባለ ቀበሌ አካባቢ የሚኖሩ ባለሱቆችና ቦዘኔዎች አንድ ነገር ያያለዘሉ:: አንድ ከወገቡ የጎበጠ፣ ከፀጉሩ የሸበተ ሽማግሌ በየቀኑ በተወሰነ ሰዓት ሽርሽር ይወጣል:: የሚሄድበት መንገድ አንድ ሆኖ ሳለ የሚሸፍነው ርቀት ግን በየቀኑ በትንሽ በትንሹ ይቀንሳል የሚራመደው በጣም ዝግ ብሉ ሲሆን አንድም ቀን ግራና ቀኝ ሳያይ እንዳቀረቀረ ወደፊት ነው የሚጓዘው
አንድ ከተወሰነ ስፍራ ሲደርስ ፊቱ ወገግ ይልና እርስ በራሱ ብቻውን ያወራል ማውራቱን ለማወቅ የሚቻለው ከንፈሮቹ ሲነቃነቁ ነው: ካልቬር ከተባለ ጎዳና ላይ ከሚገኝ አደባባይ ሲደርስ ቆም ይልና አካባቢውን ይቃኛል
" አካባቢውን ቃኝቶ ከጨረሰ በኋላ በአሳብ ተውጦ ዓይኑ እንባ ያቀርራል:
ጥቂት ካለቀሰ በኋላ በመጣበት መንገድ ይመለሳል
ቀን እያለፈ ሲሄድ አደባባዩን በሩቁ ማየት እንጂ ከእዚያ ለመድረስ አልቻለም፡ ሰውነቱ እየደከመ ሄደ:፡ ወደኋላማ ወደ አደባባዩ መጠምዘዣ መድረስ እንኳን ተሳነው፡፡ በየቀኑ በዚህ ዓይነት በተወሰነ ሰዓት ከቤቱ እየወጣ ጉልበቱ እስከፈቀደለት ድረስ ተጉዞ ይመለሳል፡፡ ዝናብ ሲሆን ጥላ ይይዛል፡ ብርድ ሲሆን ካፖርት ይለብሳል፡ የሚሸፍነው ርቀት ባጠረ ቁጥር ከደረሰበት ቆም ይልና አንገቱን ከነቀነቀ በኋላ ግራ ቀኙን ተመልክቶ ይመለሳል፡፡ ከጊዜ በኋላ የተቀነሰው መንገዱ ብቻ አልነበረም፤ የእንባውም ዘለላ ተቀነሰ፡ በመጨረሻ እስከነአካቴው ዓይኑ ደርቆ ለማልቀስ ቢፈልግም እምባ አይወጣውም:፡ በየእለቱ ሽማግሌው ብቅ ሲል አንዲት አሮጊት «የሚገርም ነው‥ ሰዓቱን ጠብቆ ይመጣል፣ አይቀራትም መቼም» ይላሉ፡
ከተወሰነ ነጥብ ሲደርስ ደግሞ ልጆች እየሳቁ ይከተሉታል
አንድ ቀን ዣን ቫልዣ ከቤቱ ወጥቶ ከዋናው ጎዳና ሲደርስ ሦስት
እርምጃ ወደፊት ከተራመደ በኋላ ከድንጋይ ላይ ቁጭ አለ፡፡ ሰኔ 5 ቀን
ከዚህች ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ ነው ጋቭሮችን ያነጋገረው:፡ ጥቂት አወጣ፣
አወረደና ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ከዚያ በኋላ ለሽርሽር መውጣት አልቻለም::
በሚቀጥለው ቀን ከክፍሉም አልወጣም:: አሁንም በሚቀጥለው ቀን ከአልጋው አልተነሳም::
👍16
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ብቻ... የለም... አልሆነም: ይኸው እዚ እኔ ብቻዬን ጣዕር ይዞ ያጣድፈኛል
ብቻዬን! ወይ አምላኬ፣ ወይ አምላኬ ስማኝ፡ ሁለተኛ አላያትም?
ልክ ይህን ሲያሰላስል በር ተንኳኳ፡
ያን እለት፤ ሰዓቱ ግን ትንሽ ቀደም ይላል፤ ዣን ቫልዣ እንደዚያ ጣዕር ይዞት ሲታገል አሽከር ለማሪየስ ደብዳቤ ያመጣለታል፡ ደብዳቤው ሲሰጠው ማስታወሻውን የሰጠው ሰው ከሳሎን ቤት እንደሚጠብቅ
ይገለጽለታል፡ ደብዳቤውን ከፍቶ አነበበው::
«ጌታዬ፣ እኔም ፈጣሪ ቢልልኝ ኖሮ ባሮን ቴናድዬ በመባል ጌታ የጌታ ልጅ ተብዬ በታወቅሁ ነበር ግን አላለልኝም፡፡ ያም ሆነ ይህ አሁን ለምትውልልኝ ውለታ ወይም ለምታደርግልኝ እርዳታ አጸፋ እመልሳለሁ፡፡»
«ስለአንድ ሰው ምሥጢር አውቃለሁ፡፡ ግለሰቡ ከሕይወትህ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ ምሥጢሩን ማወቅ ይጠቅምሃል:: እኔ ደግሞ ምሥጢሩን
ለማካፈል ፈቃደኛ ነኝ፡፡ ይህ ሰው የተከበረ ቤተሰብህን ስም የሚያጐድፍ ነው፡: ከክብርት እመቤቴም ጋር ግንኙነት ስለሌለው ከእናንተ መራቅ አለበት: ወንጀለኛው ወንጀሉ ሳይገለጥበት እንዲኖር መፍቀድ የትክክለኛ
ፍርድ ገጽታ አይደለም... ከታላቅ አክብሮት ጋር!››
ደብዳቤው ቴናድ በሚል ስም ተፈርሞአል፡
ማሪየስ በጣም ተረበሸ:: በአንድ በኩል ሲደሰት በሌላ በኩል ተከፋ፡፡ እንደ ሌሎቹ ጠቋሚዎች ሕይወቱን ያዳነለት የውሸት ስው ይዞለት የመጣ መሰለው፡፡ ለማንኛውም ከኪሱ ገንዘብ መኖሩን ካረጋገጠ በኋላ ተጣራ:
አሽከር ገባ::
«ሰውዬውን ይዘኸው ና።»
ደብዳቤውን የላከው ለው ገባ: ማሪየስ እንደ መደነቅ አለ፡፡
አሁን የገባው ሰው «ሕይወትህን ያዳነልህ ሰው ይዤ መጣሁ»
በማለት ቀደም ሲል የመጣ ሳይሆን እንግዳ ሰው ነው።
ጥቁር በጥቁር ነው የለበሰወ ጥቁር መነጽርም አድርጎአል: ከአፍንጫው ደፍጠጥ፣ ከአገጩ ረዘም ያለ ሲሆን በእጁ ባርኔጣ ይዟል።
ማሪየስ የጠበቀውን ሳይሆን ሌላ ሰው ከክፍሉ ውስጥ በመግባቱ
ከፊቱ ላይ ተስፋ የመቁረጥ ምልክት ታየበት እርሱን ያስጨነቀው ሕይወቴን ያዳነው ማን ነው የሚል ፕያቄ ሲሆን ጠብቆት የነበረው ሰው ይህን ዜና ይዞልኝ ይመጣል» ብሎ የገመተው ነበር ሰውዬውን ከእግር ጥፍር እስከ ራስ ፀጉር አጤነው::
«ምን ትፈልጋለህ?» ሲል በመኮሳተር ጠየቀው
እንግዳወ በተራው ማሪየስን አጤነው የመረበሽ መልክ አልታየበትም፡: እንዲያውም እጁን ሱሪ ኪስ ውስጥ ጨምሮ ወገቡን ሳያቀና ግምባሩን ብቻ አቅንቶ ነው ማሪየስን ያየው «ጌታዬ፣ የመጣሁበትን አስረዳለሁ:: የምሸጥልህ ምሥጢር አለኝ፡»
«ምሥጢር?»
«አዎን፣ ምስጢር»
«ቀጥል፡››
«ጌታዬ ከቤትህ ውስጥ ሌባና ነፍሰ ገዳይ አለ፡፡»
ማሪየስ ክው አለ
«እኔ ቤት ውስጥ? የለም» ሲል ጮክ ብሎ ተናገረ ነቅነቅ የማይለው ደፋሩ እንግዳ ባርኔጣውን በእጁ ጠረግ ጠረግ
አድርጎ ንግግሩን ቀጠለ፡
«እውነተኛ ስሙን ልነግርህ ነው፡፡ ስሙን በነፃ ያለ ክፍያ ነው የምገልጽልህ፡»
‹‹እየሰማሁ ነው»
«ስሙ ዣን ቫልዣ ይባላል፡፡»
«አውቀዋለሁ »
«አሁን ስነግርህ ነው ያወቅከው::»
«አይደለም፧ከዚያ በፊት አውቀዋለሁ::
እንግዳው በፈገግታ ቀጠለ፡፡
‹‹ጌታዬን መቃወም አልፈልግም፡ ለማንኛውም ብዙ ነገር ማወቄን
መገንዘብ አለብህ አሁን የምነግርህ ጉዳይ ግን እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው»
ማሪየስ እንግዳውን ትኩር ብሎ አየው::
«ዣን ቫልዣን የምሥጢር ስም ብቻ ሳይሆን የአንተንም የምሥጢር
ስም አውቃለሁ፡፡ እንዲሁም ትልቁን ምሥጢር አውቀዋለሁ
«ያንተን ስም»
«የእኔን ስም?»
«አዎን፣ ያንተን ስም:»
«ይህ እኮ አስቸጋሪ አይደለም ጌታዬ ከጻፍኩልህ ደብዳቤ ላይ ስሜን
ጽፌ የለም እንዴ?»
"
«'ዬን' አስቀርተሃል»
«እህ?»
«ቴናድዬ::»
«ማነው እሱ?»
አደጋ ሲመጣ ከሰው ጀምሮ እስከ ትንኝ ሁሉም መከላከያውን ያበጃል፡፡"
ዘበኞች ጥግ ይይዛሉ፡ ይህ ሰው ግን መሳቅ ጀመረ።
ማሪየስ ከኪሱ ገንዘብ አውጥቶ ወረወረለት:
«አመሰግናለሁ ጌታዬ! አምስት መቶ ፍራንክ!» አለ ቴናድዬ።
ቴናድዬ በመገረም ገንዘቡን አየው፧ ደባበሰው፤ መረመረው: በድጋሚ
«አምስት መቶ ፍራንክ» አለ በመደነቅ:: ቀጥሎ «ይቺ...ቺ ጥሩ ናት» አለ
በማጉረምረም:: ከዚያም በድፍረት «አሁን መነጋገር እንችላለን›› ካለ በኋላ
በጉሬሣ ፍጥነት መነጽሩን አወለቀ አንገቱ ላይ የጠመጠመውንም እስካርፍ
ፈታ፡፡ ዓይኑ በራ፤ ፊቱ አንፀባረቀ:: አፍንጫው ቀጥ አለ፡፡ ያ አስከፊ ፊቱ
ጥምብ ያየ አሞራ ይመስል ቶሎ ተቀያየረ ልክ እንደ ጥምብ አንሳ አሞራ
እርሱም ጥምብ ያገኘ መሰለው፡
«ጌታዬ መቼም አትሳሳትም» አለ ጥርት ባለ ድምፅ፤ «በእርግጥ እኔ ቴናድዬ ነኝ::»
አሁን ገና ከወገቡ ቀና አለ፡፡ በቴናድዬ አመለካከት በማሪየስና በእርሱ መካከል ገና ንግግሩ አልተጀመረም:: አካሄዱን ለውጦ አዲስ ስልት መቀየስ እንዳለበት አምኖአል፡ ጉዳዩ ብዙም አልተበላሸም:: አምስት መቶ ፍራንክ እንደሆነ ተገኝቷል
«እኔ ቴናድዬ ነኝ» ለ በኋላ ዝም ስላለ ማሪየስ ጣልቃ ይገባል፡
«ቴናድዬ፧ ስምህን ነግሬሃለሁ: አሁን አንተ በተራህ ምሥጢርህን ንገረኝ፡፡ ልትነግረኝ የመጣህበትን እኔ እንድነግርህ ትጠብቃለህ: እኔም እንዳንተው ወሬ የምሰበስብበት መንገድ አለኝ፡፡ ከአንተ ይበልጥ እንደማውቅ አሁን ትገነባለህ እንዳልከው ዣን ቫልዣ ሌባ፤ ቀማኛና ነፍሰ ገዳይ እንደሆነ አውቃለሁ መሴይ ማንደላይን የተባለውን ሁብታም ባለፋብሪካ በመዝረፉና በማክሰሩ ቀማኛ ነው የፖሊስ አዛዥ የዣቬርን ሕይወት
በማጥፋቱ ገዳይ ነው»
ቴናድዬ በተሸፈነ ሰው ዓይን ማሪየስን አየው: ነገር ግን ወዲያው አንድ መላ ስለታየው በኩራት መንፈስ አሁንም ፈገግ እያለ ተናገረ::
«ጌታዬ የተሳሳትን መሰለኝ
‹ምን!» ሲል ማሪየስ መለስ፡ «ይህን ትክዳለህ? ቃሌ እውነትን ያዘለ
ነው፡፡»
«ጌታዬ በማረጋገጥ ነው የምትናገረው፡፡ ለዚህም ስለአንተ ኩራት ይሰማኛል፡፡ ሆኖም እውነትና ትክክለኛ ፍርድ መውጣት አለባቸው:: ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ሲወነጀሉ መስማት አልፈልግም ጌታዬ፣ ዣን ቫልዣ መሱይ ማንደላይንን አልዘረፈም: ዣን ቫልዣ ዣቬርን አልገደለም»
«እንዴት ነው? ስትናገር አረጋግጠህ ነው!»
«በሁለት ምክንያት»
«በምንና በምን?»
«የመጀ…ሪያው ይኸውልህ፡ ዣን ቫልዣ መሴይ ማንደላይንን አልዘረፈም፤ ምክንያቱም ዣንቫልዣና መሴይ ማንደላይን አንድ ሰው ናቸው:፡›
‹‹ምንድነው የምትነግረኝ?»
‹‹ሁለተኛውን ምክንያት ደግሞ ስማ:: ዣቬርን አልገደለም ምክንያቱም
ዣቬርን የገደለው ራሱ ዣቬር ነው፡
«ምን ማለትህ ነው?»
«ዣቬር ራሱን ነው ያጠፋው፡»
‹ማረጋገጫ፣ ማረጋገጫ አምጣ» ሲል ማሪየስ በኃይል ጮኸ::
ቴናድዬ ቀጠለ፡፡ የሚናገረውን በማራዘም ጫን እያለ ተናገረ:
«የፖ.ሊሱ.... አዛዥ.... ዣ....ቬ...ር …ስም…ጦ ...ከጀ....ልባ .ሥር…ነው...የተገኘው...::»
«አሁንም ማስረጃ አምጣ
ነው የምልህ»
ቴናድዬ ከኪሱ ውስ ኦንድ ፖስታ አወጣ በፖስታው ውስጥ ቀለማቸው የተለያየ የተጣጠፉ ወረቀቶች ነበሩበት።
መረጃዎቼ እኮ ከእጄ ውስጥ ነው ያሉት አለ በዝግታ ስናገር ያለማስሪጃ አልናገርም ደግሞም ስለእጅ ጽሑፍ ማስረጃ አይደለም የማወራው
«እና ማስረጃዎቹ የታተሙ ናቸው።» "
ቴናዲዬ እየተናገረ ከፓስታው ውስጥ
የጋዜጣ ቁራጮችን አውጥቶ
ዘረጋ ወረቀቶቹ ፀሓይ ስለመታቸው ወደ ቢጫነት ተቀይረዋል፡ ከሁለቱ አንደኛው ቁራጭ ጫፍ ጫፉ በመበላቱና በመቀደዱ የቆየ ለመሆኑ በግልጽ
ይታወቃል::
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አምስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ብቻ... የለም... አልሆነም: ይኸው እዚ እኔ ብቻዬን ጣዕር ይዞ ያጣድፈኛል
ብቻዬን! ወይ አምላኬ፣ ወይ አምላኬ ስማኝ፡ ሁለተኛ አላያትም?
ልክ ይህን ሲያሰላስል በር ተንኳኳ፡
ያን እለት፤ ሰዓቱ ግን ትንሽ ቀደም ይላል፤ ዣን ቫልዣ እንደዚያ ጣዕር ይዞት ሲታገል አሽከር ለማሪየስ ደብዳቤ ያመጣለታል፡ ደብዳቤው ሲሰጠው ማስታወሻውን የሰጠው ሰው ከሳሎን ቤት እንደሚጠብቅ
ይገለጽለታል፡ ደብዳቤውን ከፍቶ አነበበው::
«ጌታዬ፣ እኔም ፈጣሪ ቢልልኝ ኖሮ ባሮን ቴናድዬ በመባል ጌታ የጌታ ልጅ ተብዬ በታወቅሁ ነበር ግን አላለልኝም፡፡ ያም ሆነ ይህ አሁን ለምትውልልኝ ውለታ ወይም ለምታደርግልኝ እርዳታ አጸፋ እመልሳለሁ፡፡»
«ስለአንድ ሰው ምሥጢር አውቃለሁ፡፡ ግለሰቡ ከሕይወትህ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ ምሥጢሩን ማወቅ ይጠቅምሃል:: እኔ ደግሞ ምሥጢሩን
ለማካፈል ፈቃደኛ ነኝ፡፡ ይህ ሰው የተከበረ ቤተሰብህን ስም የሚያጐድፍ ነው፡: ከክብርት እመቤቴም ጋር ግንኙነት ስለሌለው ከእናንተ መራቅ አለበት: ወንጀለኛው ወንጀሉ ሳይገለጥበት እንዲኖር መፍቀድ የትክክለኛ
ፍርድ ገጽታ አይደለም... ከታላቅ አክብሮት ጋር!››
ደብዳቤው ቴናድ በሚል ስም ተፈርሞአል፡
ማሪየስ በጣም ተረበሸ:: በአንድ በኩል ሲደሰት በሌላ በኩል ተከፋ፡፡ እንደ ሌሎቹ ጠቋሚዎች ሕይወቱን ያዳነለት የውሸት ስው ይዞለት የመጣ መሰለው፡፡ ለማንኛውም ከኪሱ ገንዘብ መኖሩን ካረጋገጠ በኋላ ተጣራ:
አሽከር ገባ::
«ሰውዬውን ይዘኸው ና።»
ደብዳቤውን የላከው ለው ገባ: ማሪየስ እንደ መደነቅ አለ፡፡
አሁን የገባው ሰው «ሕይወትህን ያዳነልህ ሰው ይዤ መጣሁ»
በማለት ቀደም ሲል የመጣ ሳይሆን እንግዳ ሰው ነው።
ጥቁር በጥቁር ነው የለበሰወ ጥቁር መነጽርም አድርጎአል: ከአፍንጫው ደፍጠጥ፣ ከአገጩ ረዘም ያለ ሲሆን በእጁ ባርኔጣ ይዟል።
ማሪየስ የጠበቀውን ሳይሆን ሌላ ሰው ከክፍሉ ውስጥ በመግባቱ
ከፊቱ ላይ ተስፋ የመቁረጥ ምልክት ታየበት እርሱን ያስጨነቀው ሕይወቴን ያዳነው ማን ነው የሚል ፕያቄ ሲሆን ጠብቆት የነበረው ሰው ይህን ዜና ይዞልኝ ይመጣል» ብሎ የገመተው ነበር ሰውዬውን ከእግር ጥፍር እስከ ራስ ፀጉር አጤነው::
«ምን ትፈልጋለህ?» ሲል በመኮሳተር ጠየቀው
እንግዳወ በተራው ማሪየስን አጤነው የመረበሽ መልክ አልታየበትም፡: እንዲያውም እጁን ሱሪ ኪስ ውስጥ ጨምሮ ወገቡን ሳያቀና ግምባሩን ብቻ አቅንቶ ነው ማሪየስን ያየው «ጌታዬ፣ የመጣሁበትን አስረዳለሁ:: የምሸጥልህ ምሥጢር አለኝ፡»
«ምሥጢር?»
«አዎን፣ ምስጢር»
«ቀጥል፡››
«ጌታዬ ከቤትህ ውስጥ ሌባና ነፍሰ ገዳይ አለ፡፡»
ማሪየስ ክው አለ
«እኔ ቤት ውስጥ? የለም» ሲል ጮክ ብሎ ተናገረ ነቅነቅ የማይለው ደፋሩ እንግዳ ባርኔጣውን በእጁ ጠረግ ጠረግ
አድርጎ ንግግሩን ቀጠለ፡
«እውነተኛ ስሙን ልነግርህ ነው፡፡ ስሙን በነፃ ያለ ክፍያ ነው የምገልጽልህ፡»
‹‹እየሰማሁ ነው»
«ስሙ ዣን ቫልዣ ይባላል፡፡»
«አውቀዋለሁ »
«አሁን ስነግርህ ነው ያወቅከው::»
«አይደለም፧ከዚያ በፊት አውቀዋለሁ::
እንግዳው በፈገግታ ቀጠለ፡፡
‹‹ጌታዬን መቃወም አልፈልግም፡ ለማንኛውም ብዙ ነገር ማወቄን
መገንዘብ አለብህ አሁን የምነግርህ ጉዳይ ግን እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው»
ማሪየስ እንግዳውን ትኩር ብሎ አየው::
«ዣን ቫልዣን የምሥጢር ስም ብቻ ሳይሆን የአንተንም የምሥጢር
ስም አውቃለሁ፡፡ እንዲሁም ትልቁን ምሥጢር አውቀዋለሁ
«ያንተን ስም»
«የእኔን ስም?»
«አዎን፣ ያንተን ስም:»
«ይህ እኮ አስቸጋሪ አይደለም ጌታዬ ከጻፍኩልህ ደብዳቤ ላይ ስሜን
ጽፌ የለም እንዴ?»
"
«'ዬን' አስቀርተሃል»
«እህ?»
«ቴናድዬ::»
«ማነው እሱ?»
አደጋ ሲመጣ ከሰው ጀምሮ እስከ ትንኝ ሁሉም መከላከያውን ያበጃል፡፡"
ዘበኞች ጥግ ይይዛሉ፡ ይህ ሰው ግን መሳቅ ጀመረ።
ማሪየስ ከኪሱ ገንዘብ አውጥቶ ወረወረለት:
«አመሰግናለሁ ጌታዬ! አምስት መቶ ፍራንክ!» አለ ቴናድዬ።
ቴናድዬ በመገረም ገንዘቡን አየው፧ ደባበሰው፤ መረመረው: በድጋሚ
«አምስት መቶ ፍራንክ» አለ በመደነቅ:: ቀጥሎ «ይቺ...ቺ ጥሩ ናት» አለ
በማጉረምረም:: ከዚያም በድፍረት «አሁን መነጋገር እንችላለን›› ካለ በኋላ
በጉሬሣ ፍጥነት መነጽሩን አወለቀ አንገቱ ላይ የጠመጠመውንም እስካርፍ
ፈታ፡፡ ዓይኑ በራ፤ ፊቱ አንፀባረቀ:: አፍንጫው ቀጥ አለ፡፡ ያ አስከፊ ፊቱ
ጥምብ ያየ አሞራ ይመስል ቶሎ ተቀያየረ ልክ እንደ ጥምብ አንሳ አሞራ
እርሱም ጥምብ ያገኘ መሰለው፡
«ጌታዬ መቼም አትሳሳትም» አለ ጥርት ባለ ድምፅ፤ «በእርግጥ እኔ ቴናድዬ ነኝ::»
አሁን ገና ከወገቡ ቀና አለ፡፡ በቴናድዬ አመለካከት በማሪየስና በእርሱ መካከል ገና ንግግሩ አልተጀመረም:: አካሄዱን ለውጦ አዲስ ስልት መቀየስ እንዳለበት አምኖአል፡ ጉዳዩ ብዙም አልተበላሸም:: አምስት መቶ ፍራንክ እንደሆነ ተገኝቷል
«እኔ ቴናድዬ ነኝ» ለ በኋላ ዝም ስላለ ማሪየስ ጣልቃ ይገባል፡
«ቴናድዬ፧ ስምህን ነግሬሃለሁ: አሁን አንተ በተራህ ምሥጢርህን ንገረኝ፡፡ ልትነግረኝ የመጣህበትን እኔ እንድነግርህ ትጠብቃለህ: እኔም እንዳንተው ወሬ የምሰበስብበት መንገድ አለኝ፡፡ ከአንተ ይበልጥ እንደማውቅ አሁን ትገነባለህ እንዳልከው ዣን ቫልዣ ሌባ፤ ቀማኛና ነፍሰ ገዳይ እንደሆነ አውቃለሁ መሴይ ማንደላይን የተባለውን ሁብታም ባለፋብሪካ በመዝረፉና በማክሰሩ ቀማኛ ነው የፖሊስ አዛዥ የዣቬርን ሕይወት
በማጥፋቱ ገዳይ ነው»
ቴናድዬ በተሸፈነ ሰው ዓይን ማሪየስን አየው: ነገር ግን ወዲያው አንድ መላ ስለታየው በኩራት መንፈስ አሁንም ፈገግ እያለ ተናገረ::
«ጌታዬ የተሳሳትን መሰለኝ
‹ምን!» ሲል ማሪየስ መለስ፡ «ይህን ትክዳለህ? ቃሌ እውነትን ያዘለ
ነው፡፡»
«ጌታዬ በማረጋገጥ ነው የምትናገረው፡፡ ለዚህም ስለአንተ ኩራት ይሰማኛል፡፡ ሆኖም እውነትና ትክክለኛ ፍርድ መውጣት አለባቸው:: ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ሲወነጀሉ መስማት አልፈልግም ጌታዬ፣ ዣን ቫልዣ መሱይ ማንደላይንን አልዘረፈም: ዣን ቫልዣ ዣቬርን አልገደለም»
«እንዴት ነው? ስትናገር አረጋግጠህ ነው!»
«በሁለት ምክንያት»
«በምንና በምን?»
«የመጀ…ሪያው ይኸውልህ፡ ዣን ቫልዣ መሴይ ማንደላይንን አልዘረፈም፤ ምክንያቱም ዣንቫልዣና መሴይ ማንደላይን አንድ ሰው ናቸው:፡›
‹‹ምንድነው የምትነግረኝ?»
‹‹ሁለተኛውን ምክንያት ደግሞ ስማ:: ዣቬርን አልገደለም ምክንያቱም
ዣቬርን የገደለው ራሱ ዣቬር ነው፡
«ምን ማለትህ ነው?»
«ዣቬር ራሱን ነው ያጠፋው፡»
‹ማረጋገጫ፣ ማረጋገጫ አምጣ» ሲል ማሪየስ በኃይል ጮኸ::
ቴናድዬ ቀጠለ፡፡ የሚናገረውን በማራዘም ጫን እያለ ተናገረ:
«የፖ.ሊሱ.... አዛዥ.... ዣ....ቬ...ር …ስም…ጦ ...ከጀ....ልባ .ሥር…ነው...የተገኘው...::»
«አሁንም ማስረጃ አምጣ
ነው የምልህ»
ቴናድዬ ከኪሱ ውስ ኦንድ ፖስታ አወጣ በፖስታው ውስጥ ቀለማቸው የተለያየ የተጣጠፉ ወረቀቶች ነበሩበት።
መረጃዎቼ እኮ ከእጄ ውስጥ ነው ያሉት አለ በዝግታ ስናገር ያለማስሪጃ አልናገርም ደግሞም ስለእጅ ጽሑፍ ማስረጃ አይደለም የማወራው
«እና ማስረጃዎቹ የታተሙ ናቸው።» "
ቴናዲዬ እየተናገረ ከፓስታው ውስጥ
የጋዜጣ ቁራጮችን አውጥቶ
ዘረጋ ወረቀቶቹ ፀሓይ ስለመታቸው ወደ ቢጫነት ተቀይረዋል፡ ከሁለቱ አንደኛው ቁራጭ ጫፍ ጫፉ በመበላቱና በመቀደዱ የቆየ ለመሆኑ በግልጽ
ይታወቃል::
👍18
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ቴናድዬ ንግግሩን የጨረሰው ቁራጩን እራፊ ከኪሱ በማውጣት ነበር ጨርቁ በደረቀ ደምና በቆሻሻ ተጨማልቋል ቀለሙ ጥቁር ሲሆን ማሪየስ እንዲያየው ወደ ዓይኑ አስጠጋለት።
ማሪየስ ብድግ አለ:: ፊቱ በአንድ ጊዜ አመድ መሰለ፡፡ መተንፈስ አቃተው፡ ዓይኑ ከጨርቁ ላይ ተተከለ: መናገር አልቻለም: ዓይኑን ከጨርቁ ሳያነሳ ወደኋላ ሸሸ፡፡ ቀኝ እጁን ከኪሱ አስገብቶ ቁልፍ አወጣ
በቁልፉ ከዚያ የነበረ አነስተኛ ቁምሣጥን ከፈተ አሁንም ዓይኑን ከቁራጩ ጨርቅ ላይ አላነሳም፡ በዚህ ጊዜ ቴናድዬ ቀጠለ።
«ጌታዬ፣ ሟቹ ወጣት በኪሱ ብዙ ገንዘብ ይዞ እንደነበረና ዣን ቫልዣ በጥበቡ አጥምዶ እንደ ገደለው ብርቱ የሆነ እምነት አለኝ፡»
«ወጣቱ የምትለው እኔው ራሴ ነኝ፤ ኮቱም ያውልህ! ሲል ማሪየስ ጩኸቱን ለቀቀው:: በደም የተጨማለቀውን ኮት ከምንጣፍ ላይ ጣለው»
ከዚያም ቁራጩን ጨርቅ ከቴናድዬ እጅ ነጠቀ:: ጎንበስ ብሎ ቁራጩን
ጨርቅና የኮቱ ቀዳዳ ይገጥሙ እንደሆነ ለካ፡፡ ጨርቁ ከቀዳዳው ልክክ በማለቱ የኮቱን ቀዳዳ በትክክል ደፈነው::
ቴናድዬ አመዱ ቡን አለ፡፡ ‹‹ተበላሁ» ሲል አሰበ፡፡
ማሪየስ ከተቀመጠበት ገንፍሎ ተነሳ:: በአሳብ ረመጥ ተቃጠለ፡፡
ቶሎ ብሎ ከኪሱ ውስጥ ገባ እጁን ከኪሱ ሳያወጣ መንቆራጠጥ ጀመረ: ግሥላ መስሎ በቀጥታ ወደ ቴናድዬ ሄደ: ከኪሱ ውስጥ ያወጣን አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ የቴናድዬን እጅ በማስነካት አሳየው
«ርኩስ ነህ! ውሸታም ነህ! ስም አጥፊ ነህ! ተንኮለኛ ነህ ምቀኛ ነህ! ይህን ሰው ለመክሰስ ነው የመጣኸው፤ ግን ትክክለኛና እውነተኛ ሰው
መሆኑን ነው የመሰከርክለት፡፡ ልታጠፋውና ስሙን ልታጕድፈው ፈልገህ
ነበር፤ ግን ክብር ነው ያጕናጸፍከው:: አንተ ነህ ሌባ! አንተ ነህ ነፍሰ ገዳይ
አንተ ነህ እንጂ እርሱ አይደለም ወደ ሆስፒታሉ ከሚወስደው ጎዳና አጠገብ ከሚገኘው ትኖርበት ከነበረው ዋሻ ውስጥ ጣራ ላይ ተንጠልጥዬ የሠራኸውን ሁሉ አይቼሃለሁ፣ ዦንድሬ! ቴናድዬ: ብፈልግ አንተን ለማሳሰር
የሚያስችል በቂ ማስረጃ አለኝ ግን
ምን ያደርግልኛል! አሁን ብቻ ከዚህ
ጥፋልኝ:፡ እንካ ለማኝ ስለሆንክ ይህን አንድ ሺህ ፍራንክ ጨምረህ ውሰድና
ውጣልኝ፡»
ገንዘቡን ወረወረለት
«ስማ ዦንድሬ! ቴናድዬ፣ አንተ እቡይ! ይህ ትምህት ሊሆንህ ይገባል የእኛ ምሥጢረኛ፣ የእኛ የጨለማ ነጋዴ፣ አንተ የተረገምክ ይህንንም አምስት መቶ ፍራንክ ወሰድና ብቻ ከዚህ ውጣልኝ ሂድ፣ ሂድ ከዚህ ቤት ውጣ ከዓይኔ ብቻ ተሰወር ደስ ይበልህ ይህን ብቻ ነው የምፈልገው ውይ ርኩስ! እንዲያውም ሦስት ሺህ ፍራንክ በተጨማሪ እንካ! ውሰዳቸው፡ አንተ ሽፍታ! ነገ ወደ አሜሪካ ትሄዳለህ እኔ ደግሞ አገር ጥለህ መሄድህን እከታተላለሁ: አገር ጥለህ ከወጣህ ሌላ ሃያ ሺ ፍራንክ እሰጥሃለሁ ሂድና እዚያው ተጨማለቅ!»
«ክቡር ጌታዬ» ሲል ቴናድዬ ግራ እንደተጋባና እንደተከዘ ምንም ነገር
ሳይገባው ገንዘቡን ተሸክሞ ሄደ
በጣም ክው ነው ያለው፤ ሆኖም ደስ ብሎታል ከአሁን በኋላ ስለዚህ
ሰው በአጭሩ ተናግረን ብናቆም ይሻላል በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በማሪየስ እርዳታ ልጁን አዜልማን ይዞና ስሙን ቀይሮ ወደ አሜሪካ ሄደ:ማሪየስ ቃል የገባለትን ገንዘብ ሰጠው: አሜሪካም ከገባ በኋላ ያ ርኩስ ጠባዩ አልለቀቀውም፡፡ ብዙ ጊዜ የደካማና የክፉ ሰው ድርጊት የደህናውን ሰው በጎ ተግባር ስለሚያበላሽና ይህም ከመጥፎ ውጤት ላይ ስለሚያደርሰው ማሪየስ በሰጠው ገንዘብ ቴናድዬ አሜሪካ ውስጥ የባሪያ ንግድ አጧጧፈበት᎓
ማሪየስ ወዲያው ቴናድዬን እንደሸኘ ኮዜት ከነበረችበት የአትክልት ቦታ እየተጣደፈ ሄደ።
«ኮዜት! ኮዜት!» ሲል ተጣራ፡ «ነይ ቶሎ በይ፤ ፍጠኝ! እንሂድ:: ባስክ ቶሎ በል ሠረገላ አስመጣ፧ ፈጠን በል! ያንተ ያለህ! ለካስ እሱ ነው ሕይወቴን ያዳናት ደቂቃ አናጥፋ፤ ቶሎ ብለሽ ነጠላ ነገር ከላይሽ ላይ ጣል አድርጊ፡፡»
ኮዜት፣ ማሪየስ ያበደ መሰላት፡ ሆኖም ትእዛዙን ተቀብላ ራስዋን በቶሎ አዘጋጀት፡
ማሪየስ መተንፈስ አቃተው የሚዘልለውን ልቡ ለማብረድ እጁን ደረቱ ላይ አኖረ: ከወዲህ ወዲያ ተንቆራጠጠ ኮዜትን ዘልሎ አቀፋት «እንጃልኝ ኮዜት! ከአሁን በኋላ የተከፋሁ ሰው ነው የምሆነው» ሲል ተናገረ::
የዣን ቫልዣን ትልቅነት፣ የዣን ቫልዣን ክቡርነት የዣን ቫልዣን ስቃይ በጉልህ ስላየ ማሪየስ ፈዘዘ ወንጀለኛው ከርኩስነት ወደ ቅዱስነት ተቀየረበት ይህም በጣም አስደነቀው:: ከሕሊናው ውስጥ የሚተራመሰው ነገር ግልጽ ሊሆንለት አልቻለም ሆኖም የዣን ቫልዣን ክቡርነት
አልተጠራጠረም
ብዙም ሳይቆይ ሠረገው መጣ ኮዜትን በመደገፍ ካሳፈራት በኋላ ራሱም ዘልሎ ከሠረገላው ላይ ወጣ
«ቶሎ በል፤ ፍጠን» ሲል ባለ ሠረገላውን አዘዘው፡፡ «የምንሄደው
አርሜ ጎዳና የቤት ቁጥር 7 ነው»
ባለሠረገላው መንገዱን ቀጠለ፡፡...
በሩ ሲንኳ ሲሰማ ዣን ቫልዣ ፊቱን አዞረ: በደከመ ድምፁ ‹‹ግቡ» አለ፡፡
በሩ ተከፈተ:፡ ኮዜትና ማሪየስ ብቅ አሉ ኮዜት ቀደም ቀደም ብላ በችኮላ በመራመድ ከክፍሉ ውስጥ ገባች ማሪየስ ግን የበሩን እጄታ ይዞ ከበሩ ላይ ቀረ
«ኮዜት!» አለ ዣን ቫልዣ ብድግ ብሎ እጆቹን ሲዘረጋቸው ተንቀጠቀጡ፡፡ እጅግ በጣም ቢዳከምም ዓይኖቹ ውስጥ የደስታ ምልክት ታየው ኮዜት በስሜት ተውጣ ከደረቱ ላይ ሄዳ ዘፍ አለች ከዚያም «አባዬ» በማለት ስትናገር ዝግ ብሎ መለሰላት፡
«ኮዜት! እውነትም እርስዋ ናት? አንቺ ነሽ እመቤቴ! አንቺው ነሽ ኮዜት? ያንተ አለህ!» ብሎ እጆችዋን ጥርቅም አድርጎ ያዘ: ቀጥሎም ያንኑ ጥያቄ በመድገም «አንቺ ነሽ ኮዜት? መጣሽ» ይቅርታ አድርገሽልኛላ!›› ሲል ተናገረ::
ማሪየስ ከዓይኑ ላይ ያቀረረው እምባ ዱብ እንዳይል በርግብግቢቱ ዓይኑን ከጨመቀ በኋላ ወደፊት ተራመደ፡፡ እንዳያለቅስ ስሜቱን በኃይል እየተቆጣጠረ በጣም በደከመ ድምፅ አባባ» አለ
«አንተም ይቅር ብለኸኛል!» አለ ዣን ቫልዣ:
ማሪየስ ቃል ለመናገር አልቻለም፡ ዣን ቫልዣ በመቀጠል አመሰግናለሁ» ሲል ተናገረ
ኮዜት ነጠላዋን ጣል አደረገች: ከዚያም የዣን ቫልዣን ሽበት ማሻሸት ጀመረች ቀጥሎም ግምባሩን ሳመችው፡ እሱም ዝም አላት እርስዋም የማሪየስን እዳ የምትከፍል እየመሰላት ማሻሸቱን ቀጠለች::
መጣሃ፣ መሴይ ፓንትመርሲ፤ ይቅር ብለኸኛላ! ሲል ዣን ቫልዣ ቀደም ሲል የተናገረውን ደገመ:፡
ዣን ቫልዣ ያለውን ደግሞ ሲናገር ማሪየስ አልቻለም፤ ፈነዳ
«ኮዜት ትሰሚያለሽ? ይሄ ነው የእርሳቸው ጠባይ! እኔን ይቅርታ ይጠይቃሉ፡፡ ኮዜት
ያደረጉልኝን ታውቂያለሽ? ሕይወቴን ያዳንዋት እኮ እርሳቸው ናቸው፡: ከዚህም
ይበልጥ ነው ያደረጉት አንቺን ለእኔ አሳልፈው ሰጥተውኛል፡ የእኔን ሕይወት ካዳኑና አንቺን ለእኔ አሳልፈው ከሰጡ
በኋላሳ ምን አደረጉ! ራሳቸውን በደሉ:: ይሄ ነው ሰው ማለት፡፡ እና ለእኔ
ለውለታቢሱ፤ ለእኔ ለረሺው፤ ለእኔ ለማይታዘንለት፤ ለእኔ ለወንጀለኛ
ምስጋና ያቀርባሉ፡ ሰማሽ ሕይወቴ ከእኚህ ሰው ጫማ ስር ተደፍታ ብትቀር እንኳን በቂ አይሆንም ያ ምሽግ፣ ያ የቆሻሻ መውረጃ፣ ጨለማ፣ ያ ስቃይ! ያ ሁሉ መከራ የተቀበሉት ለእኔ ሲሉ ነው፡፡ ሕይወቴን በሕይወታቸው ነው የዋጁት ጀግንነት፣ ደግነት፣ ድፍረትና ቅድስና ሁሉ
የእርሳቸው ቢሆን አይበዛባቸውም፡፡ ኮዜት እኚህ ፍጡር መልአክ እንጂ ሰው አይደሉም»
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
ቴናድዬ ንግግሩን የጨረሰው ቁራጩን እራፊ ከኪሱ በማውጣት ነበር ጨርቁ በደረቀ ደምና በቆሻሻ ተጨማልቋል ቀለሙ ጥቁር ሲሆን ማሪየስ እንዲያየው ወደ ዓይኑ አስጠጋለት።
ማሪየስ ብድግ አለ:: ፊቱ በአንድ ጊዜ አመድ መሰለ፡፡ መተንፈስ አቃተው፡ ዓይኑ ከጨርቁ ላይ ተተከለ: መናገር አልቻለም: ዓይኑን ከጨርቁ ሳያነሳ ወደኋላ ሸሸ፡፡ ቀኝ እጁን ከኪሱ አስገብቶ ቁልፍ አወጣ
በቁልፉ ከዚያ የነበረ አነስተኛ ቁምሣጥን ከፈተ አሁንም ዓይኑን ከቁራጩ ጨርቅ ላይ አላነሳም፡ በዚህ ጊዜ ቴናድዬ ቀጠለ።
«ጌታዬ፣ ሟቹ ወጣት በኪሱ ብዙ ገንዘብ ይዞ እንደነበረና ዣን ቫልዣ በጥበቡ አጥምዶ እንደ ገደለው ብርቱ የሆነ እምነት አለኝ፡»
«ወጣቱ የምትለው እኔው ራሴ ነኝ፤ ኮቱም ያውልህ! ሲል ማሪየስ ጩኸቱን ለቀቀው:: በደም የተጨማለቀውን ኮት ከምንጣፍ ላይ ጣለው»
ከዚያም ቁራጩን ጨርቅ ከቴናድዬ እጅ ነጠቀ:: ጎንበስ ብሎ ቁራጩን
ጨርቅና የኮቱ ቀዳዳ ይገጥሙ እንደሆነ ለካ፡፡ ጨርቁ ከቀዳዳው ልክክ በማለቱ የኮቱን ቀዳዳ በትክክል ደፈነው::
ቴናድዬ አመዱ ቡን አለ፡፡ ‹‹ተበላሁ» ሲል አሰበ፡፡
ማሪየስ ከተቀመጠበት ገንፍሎ ተነሳ:: በአሳብ ረመጥ ተቃጠለ፡፡
ቶሎ ብሎ ከኪሱ ውስጥ ገባ እጁን ከኪሱ ሳያወጣ መንቆራጠጥ ጀመረ: ግሥላ መስሎ በቀጥታ ወደ ቴናድዬ ሄደ: ከኪሱ ውስጥ ያወጣን አንድ ሺህ አምስት መቶ ፍራንክ የቴናድዬን እጅ በማስነካት አሳየው
«ርኩስ ነህ! ውሸታም ነህ! ስም አጥፊ ነህ! ተንኮለኛ ነህ ምቀኛ ነህ! ይህን ሰው ለመክሰስ ነው የመጣኸው፤ ግን ትክክለኛና እውነተኛ ሰው
መሆኑን ነው የመሰከርክለት፡፡ ልታጠፋውና ስሙን ልታጕድፈው ፈልገህ
ነበር፤ ግን ክብር ነው ያጕናጸፍከው:: አንተ ነህ ሌባ! አንተ ነህ ነፍሰ ገዳይ
አንተ ነህ እንጂ እርሱ አይደለም ወደ ሆስፒታሉ ከሚወስደው ጎዳና አጠገብ ከሚገኘው ትኖርበት ከነበረው ዋሻ ውስጥ ጣራ ላይ ተንጠልጥዬ የሠራኸውን ሁሉ አይቼሃለሁ፣ ዦንድሬ! ቴናድዬ: ብፈልግ አንተን ለማሳሰር
የሚያስችል በቂ ማስረጃ አለኝ ግን
ምን ያደርግልኛል! አሁን ብቻ ከዚህ
ጥፋልኝ:፡ እንካ ለማኝ ስለሆንክ ይህን አንድ ሺህ ፍራንክ ጨምረህ ውሰድና
ውጣልኝ፡»
ገንዘቡን ወረወረለት
«ስማ ዦንድሬ! ቴናድዬ፣ አንተ እቡይ! ይህ ትምህት ሊሆንህ ይገባል የእኛ ምሥጢረኛ፣ የእኛ የጨለማ ነጋዴ፣ አንተ የተረገምክ ይህንንም አምስት መቶ ፍራንክ ወሰድና ብቻ ከዚህ ውጣልኝ ሂድ፣ ሂድ ከዚህ ቤት ውጣ ከዓይኔ ብቻ ተሰወር ደስ ይበልህ ይህን ብቻ ነው የምፈልገው ውይ ርኩስ! እንዲያውም ሦስት ሺህ ፍራንክ በተጨማሪ እንካ! ውሰዳቸው፡ አንተ ሽፍታ! ነገ ወደ አሜሪካ ትሄዳለህ እኔ ደግሞ አገር ጥለህ መሄድህን እከታተላለሁ: አገር ጥለህ ከወጣህ ሌላ ሃያ ሺ ፍራንክ እሰጥሃለሁ ሂድና እዚያው ተጨማለቅ!»
«ክቡር ጌታዬ» ሲል ቴናድዬ ግራ እንደተጋባና እንደተከዘ ምንም ነገር
ሳይገባው ገንዘቡን ተሸክሞ ሄደ
በጣም ክው ነው ያለው፤ ሆኖም ደስ ብሎታል ከአሁን በኋላ ስለዚህ
ሰው በአጭሩ ተናግረን ብናቆም ይሻላል በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በማሪየስ እርዳታ ልጁን አዜልማን ይዞና ስሙን ቀይሮ ወደ አሜሪካ ሄደ:ማሪየስ ቃል የገባለትን ገንዘብ ሰጠው: አሜሪካም ከገባ በኋላ ያ ርኩስ ጠባዩ አልለቀቀውም፡፡ ብዙ ጊዜ የደካማና የክፉ ሰው ድርጊት የደህናውን ሰው በጎ ተግባር ስለሚያበላሽና ይህም ከመጥፎ ውጤት ላይ ስለሚያደርሰው ማሪየስ በሰጠው ገንዘብ ቴናድዬ አሜሪካ ውስጥ የባሪያ ንግድ አጧጧፈበት᎓
ማሪየስ ወዲያው ቴናድዬን እንደሸኘ ኮዜት ከነበረችበት የአትክልት ቦታ እየተጣደፈ ሄደ።
«ኮዜት! ኮዜት!» ሲል ተጣራ፡ «ነይ ቶሎ በይ፤ ፍጠኝ! እንሂድ:: ባስክ ቶሎ በል ሠረገላ አስመጣ፧ ፈጠን በል! ያንተ ያለህ! ለካስ እሱ ነው ሕይወቴን ያዳናት ደቂቃ አናጥፋ፤ ቶሎ ብለሽ ነጠላ ነገር ከላይሽ ላይ ጣል አድርጊ፡፡»
ኮዜት፣ ማሪየስ ያበደ መሰላት፡ ሆኖም ትእዛዙን ተቀብላ ራስዋን በቶሎ አዘጋጀት፡
ማሪየስ መተንፈስ አቃተው የሚዘልለውን ልቡ ለማብረድ እጁን ደረቱ ላይ አኖረ: ከወዲህ ወዲያ ተንቆራጠጠ ኮዜትን ዘልሎ አቀፋት «እንጃልኝ ኮዜት! ከአሁን በኋላ የተከፋሁ ሰው ነው የምሆነው» ሲል ተናገረ::
የዣን ቫልዣን ትልቅነት፣ የዣን ቫልዣን ክቡርነት የዣን ቫልዣን ስቃይ በጉልህ ስላየ ማሪየስ ፈዘዘ ወንጀለኛው ከርኩስነት ወደ ቅዱስነት ተቀየረበት ይህም በጣም አስደነቀው:: ከሕሊናው ውስጥ የሚተራመሰው ነገር ግልጽ ሊሆንለት አልቻለም ሆኖም የዣን ቫልዣን ክቡርነት
አልተጠራጠረም
ብዙም ሳይቆይ ሠረገው መጣ ኮዜትን በመደገፍ ካሳፈራት በኋላ ራሱም ዘልሎ ከሠረገላው ላይ ወጣ
«ቶሎ በል፤ ፍጠን» ሲል ባለ ሠረገላውን አዘዘው፡፡ «የምንሄደው
አርሜ ጎዳና የቤት ቁጥር 7 ነው»
ባለሠረገላው መንገዱን ቀጠለ፡፡...
በሩ ሲንኳ ሲሰማ ዣን ቫልዣ ፊቱን አዞረ: በደከመ ድምፁ ‹‹ግቡ» አለ፡፡
በሩ ተከፈተ:፡ ኮዜትና ማሪየስ ብቅ አሉ ኮዜት ቀደም ቀደም ብላ በችኮላ በመራመድ ከክፍሉ ውስጥ ገባች ማሪየስ ግን የበሩን እጄታ ይዞ ከበሩ ላይ ቀረ
«ኮዜት!» አለ ዣን ቫልዣ ብድግ ብሎ እጆቹን ሲዘረጋቸው ተንቀጠቀጡ፡፡ እጅግ በጣም ቢዳከምም ዓይኖቹ ውስጥ የደስታ ምልክት ታየው ኮዜት በስሜት ተውጣ ከደረቱ ላይ ሄዳ ዘፍ አለች ከዚያም «አባዬ» በማለት ስትናገር ዝግ ብሎ መለሰላት፡
«ኮዜት! እውነትም እርስዋ ናት? አንቺ ነሽ እመቤቴ! አንቺው ነሽ ኮዜት? ያንተ አለህ!» ብሎ እጆችዋን ጥርቅም አድርጎ ያዘ: ቀጥሎም ያንኑ ጥያቄ በመድገም «አንቺ ነሽ ኮዜት? መጣሽ» ይቅርታ አድርገሽልኛላ!›› ሲል ተናገረ::
ማሪየስ ከዓይኑ ላይ ያቀረረው እምባ ዱብ እንዳይል በርግብግቢቱ ዓይኑን ከጨመቀ በኋላ ወደፊት ተራመደ፡፡ እንዳያለቅስ ስሜቱን በኃይል እየተቆጣጠረ በጣም በደከመ ድምፅ አባባ» አለ
«አንተም ይቅር ብለኸኛል!» አለ ዣን ቫልዣ:
ማሪየስ ቃል ለመናገር አልቻለም፡ ዣን ቫልዣ በመቀጠል አመሰግናለሁ» ሲል ተናገረ
ኮዜት ነጠላዋን ጣል አደረገች: ከዚያም የዣን ቫልዣን ሽበት ማሻሸት ጀመረች ቀጥሎም ግምባሩን ሳመችው፡ እሱም ዝም አላት እርስዋም የማሪየስን እዳ የምትከፍል እየመሰላት ማሻሸቱን ቀጠለች::
መጣሃ፣ መሴይ ፓንትመርሲ፤ ይቅር ብለኸኛላ! ሲል ዣን ቫልዣ ቀደም ሲል የተናገረውን ደገመ:፡
ዣን ቫልዣ ያለውን ደግሞ ሲናገር ማሪየስ አልቻለም፤ ፈነዳ
«ኮዜት ትሰሚያለሽ? ይሄ ነው የእርሳቸው ጠባይ! እኔን ይቅርታ ይጠይቃሉ፡፡ ኮዜት
ያደረጉልኝን ታውቂያለሽ? ሕይወቴን ያዳንዋት እኮ እርሳቸው ናቸው፡: ከዚህም
ይበልጥ ነው ያደረጉት አንቺን ለእኔ አሳልፈው ሰጥተውኛል፡ የእኔን ሕይወት ካዳኑና አንቺን ለእኔ አሳልፈው ከሰጡ
በኋላሳ ምን አደረጉ! ራሳቸውን በደሉ:: ይሄ ነው ሰው ማለት፡፡ እና ለእኔ
ለውለታቢሱ፤ ለእኔ ለረሺው፤ ለእኔ ለማይታዘንለት፤ ለእኔ ለወንጀለኛ
ምስጋና ያቀርባሉ፡ ሰማሽ ሕይወቴ ከእኚህ ሰው ጫማ ስር ተደፍታ ብትቀር እንኳን በቂ አይሆንም ያ ምሽግ፣ ያ የቆሻሻ መውረጃ፣ ጨለማ፣ ያ ስቃይ! ያ ሁሉ መከራ የተቀበሉት ለእኔ ሲሉ ነው፡፡ ሕይወቴን በሕይወታቸው ነው የዋጁት ጀግንነት፣ ደግነት፣ ድፍረትና ቅድስና ሁሉ
የእርሳቸው ቢሆን አይበዛባቸውም፡፡ ኮዜት እኚህ ፍጡር መልአክ እንጂ ሰው አይደሉም»
👍15