#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹አይ እንግዲያው እኔም አልደከመኝም…ካንቺ ጋር ዞር ዞር ብል ይሻለኛል›› አላትና አብሯት ወደፊት መጓዝ ጀመረ..ፈገግ አለች…ከእሷ ጋር መለያየት ስላልፈለገ እንጂ እንደደከመው ሁኔታውን አይቶ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል…ሰዎች ካሉበት አካባቢ አንድ 200 ሜትር ያህል ርቀው ከተጓዙ በኃላ ዞር ያለ እና ለመቀመጥ ምቹ የሆነ ቦታ ስታገኝ ቀድማው ሄደችና ቁጭ አለች…ከዚህ በላይ አድክማ ልታማርረው አልፈለገችም›፡፡በረጅሙ ተነፈሰና መሬቱ ላይ ከጎኗ ተቀመጠ..
‹‹እሺ ሶፊ…ሀገራችሁ ያምራል››አላት
‹‹እርግጥ አህጉሩ የእኔ ነው…ግን ሀገሬ እዚህ አይደለም››
‹‹እና ከየት ነሽ?››
‹‹ኢትዬጵያን ታውቀታለህ?››
በአግራሞት አይኑን ከፈተ ..ምን እንዳስደነገጠው አልተገለፀላትም….‹‹ሺ ውቃያኖስ አቆርጦ የመጣው ሳያስደንቅ እኔ ከዚህች ከኢትዬጳያ መምጣት እንዴት ሊያስገርመው ቻለ?›› ብላ በውስጧ ጠየቀች፡፡
‹‹ኢትዬጵያን አውቃታለሁ በደንብ…..ጎንደርን አክሱምን፤አዲሰአባን በደንብ አውቃቸዋለሁ››አላት
‹ደሎመናንስ?›
‹‹ደሎ መና …ታሪካዊ ቦታ ነች?››
‹‹አዎ እኔን ያበቀለች ለምለምና ልዩ ቦታ ነች›አለቸው ፡፡እሱ ኢትዬጵያን አውቃታለሁ ብሎ የጠቀሳቸው ገናና ቦታዎች እሷ በጥቂቱ ታሪካቸውን እንጂ በአካል አታውቃቸውም…እሷ አብጠርጥራ የምታውቃቸውንና ተወልዳ ያደገችባቸውን ቦታዎቸ ደግሞ እሱ አያውቃቸውም ፤አረ ምን ማወቅ ብቻ ስማቸውን እንኳን በስህተት ሰማቷቸው አያውቅም፡፡
ግን ሲያወራ አይኑ ላይ ያነበበችው የራስ መተማመን መላ ኢትዬጳያን አብጠርጥሮ እንደሚያውቅ ነው፡ከዚህ ጉዞ እንደተመለሰች በቀጣይ ሰሜን ኢትዬጵያን ሄዳ መጎብኘት እንዳለባት እዛው ወሰነችና..ሰለ ደሎ መና እና ስለጠቅላላ የደቡብ ኢትዬጵያ አካባቢዎች፤ባሌ ፤ቦረና ፤ሱማሌ፤ ኬንያ ፤ሲዳሞ በትና ስታስረዳው እሱም በአድናቆት አፉን ከፍቶ አዳመጣትና ወደፊት ቦታዎቹን ለማየት እንደሚሞክር ነገራት፡፡
‹‹ይሄ ጉዞዬ የተለየ እንደሚሆን ገና ከመነሳቴ በፊትም ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነበር››
‹‹እና ወደድከው፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ ..?.ለአመታት ስመኘው የነበረ የህይወቴ ትልቁ ጉዞ እንዲህ በስኬት አጠናቅቄ ተደስቼ ሳልጨርስ አንቺን የመሰለች መላአክ መሳይ ወጣት ተዋወቅኩ››ሲላት ቅድም እንዳገኘችው ሲሰማት የነበረ አዲስ አይነት ስሜት መልሶ ተሰማት…፡፡
እኔም ስለገኘሁህ ደስ ብሎኛል…ሀገርህ ግን የት ነው?›ስትል ጠየቀችው…ሀገሩ የትም ቢሆን ግድ የላትም….የራሷን የተዘበራረቀ ስሜት ለማስተካከል ጊዜ ለማግኘት ብላ ነው ጥያቄውን የሰነዘረችው፡፡
‹‹አውስትራሊያ ነው..ግን እናቴ አሜሪካዊ ስለሆነች እዛም ብዙ ኖሪያለሁ››
‹‹አይ አሪፍ ነው…አንድ ቀን አውስትራሊያን ለማየት ስመጣ አገኝህ ይሆንል?››
‹‹በጣም ደስ ይለኛል..››እንደዚህ እያወሩ ድንገት በተተተት ብሎ የሚመጣ ነገር ሰሙ..እሱ ደንግጦ ተለጠፈባትና ወደራሱ አጣብቆ አቀፋት …እሷ ፈርታ ሳይሆን መታቀፏ በጣም አስደስቶት አንገቱ ስር ውሽቅ ብላ ትንፋሿን በጀሮ ለቀቀችበት..ስራቸው ዷ. ብሎ የሆነ ነገር ወደቀ…እንደምንም ድፍረቱን አስባስቦ ሲያየው ቅድም ያገኛት ቦታ ጥለውት የመጡት የእሷን ሻንጣ ነው…እንደምንም እራሱን አረጋጋና ከእቅፉ እሷን በማላቀቅ ሻንጣውን አምጥቶ ስራቸው በመወርወር ያስደነገጣቸውን ሰው ለማየትና ፤ ስላስደነገጣቸው ለመውቀስ ዙሪያ ገባውን ቢመለከት የሰው ዘር በአካባቢው የለም….ዞር ሲል ከበላያቸው ባለ ጉብታ ላይ ቅድም ያየው ንስር ጉብ ብሎ በመቀመጥ ወደእሱ አፍጥጦበታል፡፡
‹‹አንቺ ያወራሺኝ እውነትሽን ነው እንዴ?››
‹‹ምኑ?››
‹‹ስለንስሩ ቅድም የነገርሺኝ …ይሄንን ሻንጣ ይዞልሽ የመጣው እሱ ነው?›
‹‹ሻንጣው ቀላል ነው…እኔንም ጨምሮ ከኢትዬጵያ ድረስ ይዞኝ የመጣው እኮ እሱ ነው››
‹‹እየቀለድኩ እኮ አይደለም?››
ይሄንን ሰው ወዳዋለች…እናም ልታስደምመውና ይበልጥ ልቡንም ቀልቡንም ለመቆጣጠር ፈልጋላች፡፡
ቋንቋዋን ወደ ኦሮሚኛ ቀየረችና ‹‹ጀግናዬ ..ሰውያችን እንዴት ነው?›› ስትል ጠየቀችው፡፡አእምሮውን ከፈተላትና ስለእሱ በወፍ በር አስቃኛት… የዩኒቨርሲቲ መምህር ነው፤ሁለት መፅሀፎች የፃፈ ደራሲም ነው፤አለገባም ግን ሴት አውል ነው፡፡ሴት ወደ ህይወቱ ስቦ ሲያስገባ ሰዓታት አይፈጅበትም…ሲቀበልም ደግሞ በሙሉ ፍቅር እና ለጋሰነት ነው፤እንክብካቤውም ወደር አልባ ነው፤ግን ደግሞ መልሶ ገፍትሮ ከልቡ ሲያወጣ አንድ ወር አይፈጅበትም፤ንስሯ የነገራት መረጃ መስማት ስለፈለገችው ጉዳይ ብቻ ነው፡፡ከዚህ በፊት ስለእንደዚህ አይነት ጉዳይ የሰውን ታሪክ ልባቸው ውስጥ ገብቶ እንዲሰልልላት ጠየቃው አታውቅም… ወንዶችንም በተመለከተ በራሷ ያለት ልምድ ለዜሮ የቀረበ በመሆነ ባህሪውን ከሌላ ወንድ ጋር ልታነፃፅርና ፍርድ ልትሰጥ አትችልም…ደግሞ እሷ ከእሱጋር ቢበዛ 3 ቀን ብቻ ነው ልታሳለፍ የሚትችለው፡፡በዛ ሶስት ቀን የሚታወስና ሚያዝናና ቀን ከእሱ ጋር ካሳለፈች ከዛ በኃላ ለእድሜ ልክም አታገኘውም፡፡ ስለዚህ የእሱ ታማኝነት እና አለመታመን እንደማያስጨንቃት እራሷን አሳመነች..ንስሯ እዚህ ላይ አንድ ተንኮል ሰራባት ፤ሳትጠይቀው የብልቱን መወጣጠር በእመሮዋ ላይ ቦግ ብልጭ ቦግ ብልጭ እያደረገ አሳያት ..አፈረቸና በፈግግታ እንደታጀበች ፊቷን አዙራ አቀረቀረች..
‹‹ምን እየሆንሽ ነው..?ብቻሽን ትስቂያለሽ እንዴ?››
‹‹ንስሬ እኮ ነው››
‹‹ንስርሽ እኮ አርፎ ተቀምጦል …ምንም አይነት እንቅስቃሴ እያደረገ አይደለም››
‹‹ባክህ በእምሮዬ የሚያስቅ መልዕክት ልኮልኝ ነው››
‹‹ምን አይነት መልዕክት.እስቲ ልስማው?››
‹‹ስለአንተ ነው››
ይበልጥ ደንግጦ‹ስለእኔ ምን?››
‹‹ሴት ይወዳል እያለኝ ነው››
‹‹ይሄ ያንቺ ግምት ነወ››
‹‹የብልትህን ተገትሮ መቆሙን አሳይቶኛል››
ቶሎ ብሎ አይኖቹን ወደእግሮቹ መካከል ላከና አቀማመጡን አስተካከለ
‹‹ምትገርሚ ሰው ነሽ…እሱንም አይተሸ ነው…አንቺን ከመሰለች ውብ አፍሪካዊት ሴት ጎን ተቀምጬ ባይቆምብኝ ነው የሚገርመው››አላት፡፡
‹‹ካትሪንን ነው ወይስ ሱዛናን ማናቸውን ነበር ይበልጥ የምትወደው?››
ሆን ብላ የምትለውን እንዲያምናት ነው የቅርብ ጊዜ የፍቅር ተጣማሪው የነበሩትን ሴቶች ስም የጠራችለት፡፡ምንም ሳይናገር ዝም ብሎ አፍጥጦ ያያት ጀመር…. የሚያያት በአድናቆት ብቻ ሳይሆን በፍራቻም ጭምር ነው፡፡
‹‹ጀግናዬ አንዴ ሽንቴ መጥቷል እታች ወደ ጨካው አካባቢ ትወስደኛለህ?›› ስትለው ንስሩ ከለበት ቋጥኝ ክንፉን እያማታ ወደላይ ተነሳና መልሶ ዳይቪ ገንዳ ውስጥ እንደሚገባ ዋናተኛ ወደታች እየተምዘገዘገ መጥቶ ከተቀመጠችበት ደረሰና እሷን ማጅራቷን ይዞ ወደ ላይ አንጠልጥሏት ሲነሳ እሱ በድንጋጤ አደጋ ላይ የወደቀች መስሎት ሊያስጥላት እግሯን ለመያዝ ቢሞክርም ንስሩ ከወዲህ ወዲያ እያወናጨፈ ሸወደውና ሙሉ በሙሉ ወደላይ ይዟት በመነሳት በጉም በተሸፈነው ሰማይ ውስጥ ይዟት ገባ.፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹አይ እንግዲያው እኔም አልደከመኝም…ካንቺ ጋር ዞር ዞር ብል ይሻለኛል›› አላትና አብሯት ወደፊት መጓዝ ጀመረ..ፈገግ አለች…ከእሷ ጋር መለያየት ስላልፈለገ እንጂ እንደደከመው ሁኔታውን አይቶ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል…ሰዎች ካሉበት አካባቢ አንድ 200 ሜትር ያህል ርቀው ከተጓዙ በኃላ ዞር ያለ እና ለመቀመጥ ምቹ የሆነ ቦታ ስታገኝ ቀድማው ሄደችና ቁጭ አለች…ከዚህ በላይ አድክማ ልታማርረው አልፈለገችም›፡፡በረጅሙ ተነፈሰና መሬቱ ላይ ከጎኗ ተቀመጠ..
‹‹እሺ ሶፊ…ሀገራችሁ ያምራል››አላት
‹‹እርግጥ አህጉሩ የእኔ ነው…ግን ሀገሬ እዚህ አይደለም››
‹‹እና ከየት ነሽ?››
‹‹ኢትዬጵያን ታውቀታለህ?››
በአግራሞት አይኑን ከፈተ ..ምን እንዳስደነገጠው አልተገለፀላትም….‹‹ሺ ውቃያኖስ አቆርጦ የመጣው ሳያስደንቅ እኔ ከዚህች ከኢትዬጳያ መምጣት እንዴት ሊያስገርመው ቻለ?›› ብላ በውስጧ ጠየቀች፡፡
‹‹ኢትዬጵያን አውቃታለሁ በደንብ…..ጎንደርን አክሱምን፤አዲሰአባን በደንብ አውቃቸዋለሁ››አላት
‹ደሎመናንስ?›
‹‹ደሎ መና …ታሪካዊ ቦታ ነች?››
‹‹አዎ እኔን ያበቀለች ለምለምና ልዩ ቦታ ነች›አለቸው ፡፡እሱ ኢትዬጵያን አውቃታለሁ ብሎ የጠቀሳቸው ገናና ቦታዎች እሷ በጥቂቱ ታሪካቸውን እንጂ በአካል አታውቃቸውም…እሷ አብጠርጥራ የምታውቃቸውንና ተወልዳ ያደገችባቸውን ቦታዎቸ ደግሞ እሱ አያውቃቸውም ፤አረ ምን ማወቅ ብቻ ስማቸውን እንኳን በስህተት ሰማቷቸው አያውቅም፡፡
ግን ሲያወራ አይኑ ላይ ያነበበችው የራስ መተማመን መላ ኢትዬጳያን አብጠርጥሮ እንደሚያውቅ ነው፡ከዚህ ጉዞ እንደተመለሰች በቀጣይ ሰሜን ኢትዬጵያን ሄዳ መጎብኘት እንዳለባት እዛው ወሰነችና..ሰለ ደሎ መና እና ስለጠቅላላ የደቡብ ኢትዬጵያ አካባቢዎች፤ባሌ ፤ቦረና ፤ሱማሌ፤ ኬንያ ፤ሲዳሞ በትና ስታስረዳው እሱም በአድናቆት አፉን ከፍቶ አዳመጣትና ወደፊት ቦታዎቹን ለማየት እንደሚሞክር ነገራት፡፡
‹‹ይሄ ጉዞዬ የተለየ እንደሚሆን ገና ከመነሳቴ በፊትም ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነበር››
‹‹እና ወደድከው፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ ..?.ለአመታት ስመኘው የነበረ የህይወቴ ትልቁ ጉዞ እንዲህ በስኬት አጠናቅቄ ተደስቼ ሳልጨርስ አንቺን የመሰለች መላአክ መሳይ ወጣት ተዋወቅኩ››ሲላት ቅድም እንዳገኘችው ሲሰማት የነበረ አዲስ አይነት ስሜት መልሶ ተሰማት…፡፡
እኔም ስለገኘሁህ ደስ ብሎኛል…ሀገርህ ግን የት ነው?›ስትል ጠየቀችው…ሀገሩ የትም ቢሆን ግድ የላትም….የራሷን የተዘበራረቀ ስሜት ለማስተካከል ጊዜ ለማግኘት ብላ ነው ጥያቄውን የሰነዘረችው፡፡
‹‹አውስትራሊያ ነው..ግን እናቴ አሜሪካዊ ስለሆነች እዛም ብዙ ኖሪያለሁ››
‹‹አይ አሪፍ ነው…አንድ ቀን አውስትራሊያን ለማየት ስመጣ አገኝህ ይሆንል?››
‹‹በጣም ደስ ይለኛል..››እንደዚህ እያወሩ ድንገት በተተተት ብሎ የሚመጣ ነገር ሰሙ..እሱ ደንግጦ ተለጠፈባትና ወደራሱ አጣብቆ አቀፋት …እሷ ፈርታ ሳይሆን መታቀፏ በጣም አስደስቶት አንገቱ ስር ውሽቅ ብላ ትንፋሿን በጀሮ ለቀቀችበት..ስራቸው ዷ. ብሎ የሆነ ነገር ወደቀ…እንደምንም ድፍረቱን አስባስቦ ሲያየው ቅድም ያገኛት ቦታ ጥለውት የመጡት የእሷን ሻንጣ ነው…እንደምንም እራሱን አረጋጋና ከእቅፉ እሷን በማላቀቅ ሻንጣውን አምጥቶ ስራቸው በመወርወር ያስደነገጣቸውን ሰው ለማየትና ፤ ስላስደነገጣቸው ለመውቀስ ዙሪያ ገባውን ቢመለከት የሰው ዘር በአካባቢው የለም….ዞር ሲል ከበላያቸው ባለ ጉብታ ላይ ቅድም ያየው ንስር ጉብ ብሎ በመቀመጥ ወደእሱ አፍጥጦበታል፡፡
‹‹አንቺ ያወራሺኝ እውነትሽን ነው እንዴ?››
‹‹ምኑ?››
‹‹ስለንስሩ ቅድም የነገርሺኝ …ይሄንን ሻንጣ ይዞልሽ የመጣው እሱ ነው?›
‹‹ሻንጣው ቀላል ነው…እኔንም ጨምሮ ከኢትዬጵያ ድረስ ይዞኝ የመጣው እኮ እሱ ነው››
‹‹እየቀለድኩ እኮ አይደለም?››
ይሄንን ሰው ወዳዋለች…እናም ልታስደምመውና ይበልጥ ልቡንም ቀልቡንም ለመቆጣጠር ፈልጋላች፡፡
ቋንቋዋን ወደ ኦሮሚኛ ቀየረችና ‹‹ጀግናዬ ..ሰውያችን እንዴት ነው?›› ስትል ጠየቀችው፡፡አእምሮውን ከፈተላትና ስለእሱ በወፍ በር አስቃኛት… የዩኒቨርሲቲ መምህር ነው፤ሁለት መፅሀፎች የፃፈ ደራሲም ነው፤አለገባም ግን ሴት አውል ነው፡፡ሴት ወደ ህይወቱ ስቦ ሲያስገባ ሰዓታት አይፈጅበትም…ሲቀበልም ደግሞ በሙሉ ፍቅር እና ለጋሰነት ነው፤እንክብካቤውም ወደር አልባ ነው፤ግን ደግሞ መልሶ ገፍትሮ ከልቡ ሲያወጣ አንድ ወር አይፈጅበትም፤ንስሯ የነገራት መረጃ መስማት ስለፈለገችው ጉዳይ ብቻ ነው፡፡ከዚህ በፊት ስለእንደዚህ አይነት ጉዳይ የሰውን ታሪክ ልባቸው ውስጥ ገብቶ እንዲሰልልላት ጠየቃው አታውቅም… ወንዶችንም በተመለከተ በራሷ ያለት ልምድ ለዜሮ የቀረበ በመሆነ ባህሪውን ከሌላ ወንድ ጋር ልታነፃፅርና ፍርድ ልትሰጥ አትችልም…ደግሞ እሷ ከእሱጋር ቢበዛ 3 ቀን ብቻ ነው ልታሳለፍ የሚትችለው፡፡በዛ ሶስት ቀን የሚታወስና ሚያዝናና ቀን ከእሱ ጋር ካሳለፈች ከዛ በኃላ ለእድሜ ልክም አታገኘውም፡፡ ስለዚህ የእሱ ታማኝነት እና አለመታመን እንደማያስጨንቃት እራሷን አሳመነች..ንስሯ እዚህ ላይ አንድ ተንኮል ሰራባት ፤ሳትጠይቀው የብልቱን መወጣጠር በእመሮዋ ላይ ቦግ ብልጭ ቦግ ብልጭ እያደረገ አሳያት ..አፈረቸና በፈግግታ እንደታጀበች ፊቷን አዙራ አቀረቀረች..
‹‹ምን እየሆንሽ ነው..?ብቻሽን ትስቂያለሽ እንዴ?››
‹‹ንስሬ እኮ ነው››
‹‹ንስርሽ እኮ አርፎ ተቀምጦል …ምንም አይነት እንቅስቃሴ እያደረገ አይደለም››
‹‹ባክህ በእምሮዬ የሚያስቅ መልዕክት ልኮልኝ ነው››
‹‹ምን አይነት መልዕክት.እስቲ ልስማው?››
‹‹ስለአንተ ነው››
ይበልጥ ደንግጦ‹ስለእኔ ምን?››
‹‹ሴት ይወዳል እያለኝ ነው››
‹‹ይሄ ያንቺ ግምት ነወ››
‹‹የብልትህን ተገትሮ መቆሙን አሳይቶኛል››
ቶሎ ብሎ አይኖቹን ወደእግሮቹ መካከል ላከና አቀማመጡን አስተካከለ
‹‹ምትገርሚ ሰው ነሽ…እሱንም አይተሸ ነው…አንቺን ከመሰለች ውብ አፍሪካዊት ሴት ጎን ተቀምጬ ባይቆምብኝ ነው የሚገርመው››አላት፡፡
‹‹ካትሪንን ነው ወይስ ሱዛናን ማናቸውን ነበር ይበልጥ የምትወደው?››
ሆን ብላ የምትለውን እንዲያምናት ነው የቅርብ ጊዜ የፍቅር ተጣማሪው የነበሩትን ሴቶች ስም የጠራችለት፡፡ምንም ሳይናገር ዝም ብሎ አፍጥጦ ያያት ጀመር…. የሚያያት በአድናቆት ብቻ ሳይሆን በፍራቻም ጭምር ነው፡፡
‹‹ጀግናዬ አንዴ ሽንቴ መጥቷል እታች ወደ ጨካው አካባቢ ትወስደኛለህ?›› ስትለው ንስሩ ከለበት ቋጥኝ ክንፉን እያማታ ወደላይ ተነሳና መልሶ ዳይቪ ገንዳ ውስጥ እንደሚገባ ዋናተኛ ወደታች እየተምዘገዘገ መጥቶ ከተቀመጠችበት ደረሰና እሷን ማጅራቷን ይዞ ወደ ላይ አንጠልጥሏት ሲነሳ እሱ በድንጋጤ አደጋ ላይ የወደቀች መስሎት ሊያስጥላት እግሯን ለመያዝ ቢሞክርም ንስሩ ከወዲህ ወዲያ እያወናጨፈ ሸወደውና ሙሉ በሙሉ ወደላይ ይዟት በመነሳት በጉም በተሸፈነው ሰማይ ውስጥ ይዟት ገባ.፡፡
👍97😁12❤7👏2🔥1🥰1😱1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ከሶስት አመት በኃላ..
እናትዬውን አሳምና ከደሎ ለቃ ስትወጣ አንድ ሻንጣ ልብሷን ይዛ በትራንስፖርት ሳይሆን በንስሯ አማካይነት እየበረረች ነበር የተጓዘችው..በእጇ እናቷ ያስጨበጠቻትን 2000 ሺ ብር እና አጎቷ የሰጣትን 5 ሺ ብር .. በቃ ይሄንን ነው የያዘችው፡፡ግን ሻንጣዋ ውስጥ ከአመታት በፊት ኪኒማጀሮን ለመጓብኘት በሄደች ጊዜ ንስሯ ከባህር ወንበዴዎች ነጥቆ የሰጣት ዳይመንድ እንደቀልድ እንዳስቀመጠችው ስለነበረ ይዛው ነበር.። አዲስ አበባ እንደገቡ በደላላ 45 ሚሊዬን ብር ተሸጠ.
በ25 ሚሊዬን ብር ለገጣፎ ከተማ አካባቢ ምታርፍበት የራሷ የሆነ 2ሺ ካ.ሬ ሜትር ግቢ ላይ ጥጉን ይዞ የታነፀ ባለአምስት ክፍል ቢላ ቤት ገዝታ ከንስሯ ጋር የብቸኝነት ኑሮ መኖር ጀመረች፡፡
እንደመጣች ሰሞን ብቸኝነቱ በጣም ከብዷት ነበር.. የምታውቀው ሰው በዙያዋ ካለመኖሩም በተጨማሪ ከደንና ጫካ ውስጥ ወጥቶ በፎቅና በመኪና የታጠረ አካባቢ መኖር በጣም ሚረብሽ ሆኖባት ነበር…ቆይቶ ግን እየለመደችው መጣች፡የገዛችውንም ጊቢ እንደምትፈልገው አደረገችው….እነሆ አሁን ከሶስት አመት በኃላ ከቤቱ ይልቅ በግቢ ውስጥ ያሉ ዛፎች ዕጻዋቶች እና ፍራፍሬዎች ይበልጥ ያስደምማሉ፡፡ በግቢዋ ውስጥ ከ1140 በላይ የዕፅዋት አይነቶች ይገኛሉ፡፡ከነዚህ ውስጥ 83ቱን ከተለያዩ አህጉራት በዞረችባቸው ወቅት ቀልቧን ስበውት ወይም አስደምመዋት አምጥታ የተከለቻቸው ናቸው፡፡እርግጥ አምጥታ የተከለቻቸው ከዚህ አሁን ከተጠቀሰው ቁጥር በሶስት እጥፍ ከፍ ያለ ነበር..ከአዲስ አበባ የአየር ፀባይ ጋር ተላምደው መጽደቅ የቻሉት ግን እነዚህ ብቻ ናቸው፡፡
ግቢዋ ውስጥ ያሉ ዕጽዋቶች ሁሉ አስደማሚነታቸው ለአይን መስብ ከመሆናቸው እና ንጽህ አየር ሚያመርቱ መንፈሳዊ ማሽኖች ስለሆኑ ብቻ አይደለም እዚህ ግቢ የመትከል ተተክሎም የመብቀል እድል ያገኙት…እያንዳንዱ የተለየ ሚስጥር እና ጥበብ የሚገለጽባቸው የእግዚያብሄርን ሚስጥራዊ ሹክሹክታ በቅጠሎቻቸው እና በስሮቻቸው ነስለሚተነፍሱ ነው…::መድሀኒት ናቸው… ታአምራትን የሚሰራባቸው ናቸው..ብዙ ብዙ ነገር…በየዛፎች ቅርንጫፍች ላይ ቁጥራቸውን የማይታወቅ የወፍ ጎጆዎች ሞልተውባቸዋል፤ሶስት ጉሬዛ እና አራት ዝንጀሮዎችም አሏት ..ሁሉንም ያመጣቻው ከሀገሯ ጫካ ነው… ከደሎ መና፡፡እንደዛ ያደረገችው..ልጅነቷን ስለሚያስታውሷት ነው.እንደዛ ያደረገችው..አብራቸው እነሱን እያየች ከእነሱ እየተጫወተች ስላደገች ዘመዷቾ ስለሚመስሏት ነው… ስለምትወዳቸውና ከእነሱ ውጭ ህይወት ስለማይታያት ነው.. ስለምትወዳቸውና የሚወዷትም ስለሚመስላት ነው፡፡
አብረዋት የሚኖሩ አንድ የስልሳ ሁለት አመት አዛውንት ሰውዬ አሉ፡፡ጋሽ ተክለወልድ ይማም ይባላሉ፡፡ይሄንን ጊቢ እንዲህ ያሳመረችውም የምታስተዳድረውም ከእሳቸው ጋር ነው፡፡
እሷ ያው አብዝታ ከአንድ የምድር ጫፍ ወደሌላው መስፈንጠር የዘወትር ድርጊቷ ስለሆነ በሌለችበት ጊዜ እሳቸው ናቸው ሙሉ ሀላፊነቱን የሚወስዱላት፡፡ ዘበኛ ወይም አትክልተኛ አይደሉም፡፡ከዕጽዋቶች ጋር በፍቅር የወደቁ ከሀለማያ ዩኒቨርሲቲ ለ32 ዓመት ያስተማሩና በቅርቡ ጡረታ የወጡ የዕጽዋት ሳይንስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡
ሌላው በዋናነት ለብቸኝነቷ መድሀኒት የሆናት ንስሯ ነው ፡፡ የንስሯ እና የእሷ ግንኙነት ለሌላ ሰው ለማስረዳት ቀላል መንገድ የለም፡፡ እያንዳንዱ የሰው ልጅ እንዲጠብቀው እንዲንከባከበው እና ከክፉ ነገር እንዲከልለው ከፈጣሪው የተመደበለት ጠባቂ መልዐክ አለው ተብሎ በአብዛኛው ሰው ይታመናል፡፡ግን እነዚህ ጠባቂ መላዕክቶች አካል አልባ መንፈስ ናቸው ፡፡አይታዩም፤መታየት ብቻ ሳይሆን አብዛኛው ሰውም ጠባቂ መልአኩን በትከሻው ላይ ተሸክሞ እንደሚዞር አያውቅም… አያምንምም፡፡ስለዚህ አይገለገልባቸውም …አያዳምጣቸውም፡፡ሰው በጨለማ ውስጥ ሲጓዝ ማጅራት መቺ ከኃላው ካለ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ሳይሰማ ትከሻዬን ከበደኝ ይላል፤ያ ምን ማለት ነው? ለሚያምንበት ሰው ጠባቂ መላዕክ የማስጠንቂያ ደውል ነው…. እሱ ያልተመለከተውን በጭለማ ውስጥ የተሸሸገውን አጥቂውን ጠባቂ መልአኩ አይቶት ሹክ ብሎታል ማለት ነው፡፡እንግዲህ ያ ሰው ብልህ ከሆነ ማድረግ ያለበት መልዕክቱን አምኖ ተፈትልኮ በመሮጥ ማምለጥ ወይም ጥቃቱን ለመመከት እራሱን ማዘጋጀት ነው፡፡አይ ዝም ብሎ ተራ ፍራቻ ነው ብሎ የደረሰውን መልዕክት ችላ ብሎ በእንዝላልነቱ ከገፋበት ግን ማጃራቱን ተመቶ ይዘረራልም..ይዘረፋልም ማለት ሊሆን ይችላል፡፡
እና ለእሷ ይሄ ንስር አሞራ ጠባቂ መላዕኳ በሉት፡፡በአካል አብሯት የሚንቀሳቀስ የሚያወራት የምታወራው ጠባቂ መልአክ ስላለት፡፡የፈለገችበት የአለም ጥግ አንጠልጥሎ የሚወስዳት...ከሚንቀለቀል እቶን እሳት ውስጥ ብትገባ እንኳን አንጠልጥሎ በማውጣት ሀይቅ ውስጥ ጨምሮ የሚያቀዘቅዘት፡፡ካለሀሪ በረሀ ላይ ወስዶ በጥም ጉሮሮዋ ከደረቀ ከመንቁሩ ወይን አመንጭቶ የሚያጠጣት…..ከፈለገች የሲ.አይ .ኤን የስለላ መረብ በጣጥሶ የዋይት ሀውስ ራት ግብዝ ላይ አስገብቶ የሚጥላት፡፡ሱፐር ሂዩማን እንድትሆን ሱፐር ሆኖ ሱፐር የሚያደርጋት መልዐኳ ነው፡፡የማታውቀው አባቷ ስጦታ፡ከሀገሯ አብሮት የተሰደ የደስታዋም ሆነ የሀዘኗ ጊዜ ተጋሪዋ፡፡
በንስራ አካል ውስጥ ባለው የነቃና የበቃ ነፍስ እገዛ እሱ ያየውን አንደምታይ እና ያሰበውን እንዳምታስብ ታውቃለች፡፡ልክ በአንድ ዲኮደር እንደሚሰራ ሁለት ቴሌቪዝን በሉን….እሷ ቤቷ ቁጭ ብላ እሱ አየሩን ሰንጥቆ በሚበርበት የምድር ጥግ ሁሉ እያየ ያለውን ነገር ጥርት ባለ ምስል በአዕምሮዋ ታያለች…የንስርን አይን ደግሞ የሚታውቅ ነው..እያንዳንዱ ንስር ቅንጣት በቀላሉ በአይኑ ሌንስ ይቀልባታል፡፡ይሄ ገለጻ ለብዙዎችን ግራ ሊያጋባ ይችላል፡፡
ይሄ መልአክ ነው ሰይጣን የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል፡፡መልአክ ከሆነ ለምን በእርግብ አካል ውስጥ አላደረም ወይንም እንደተለመደው ለምን የበግ ስጋና ቆዳ አለበሰም፡፡እሱን የሚያውቀው ይሄ እንዲሆን ያደረገው የማታውቀውና የሌላ አለም ፍጡር የሆነው አባቷ ነው፡፡ለእሷ ግን ምንም ግድም አይሰጣትም፡፡ዋናው በእርግጠኝነት የምታውቀው ነገር የእሷ እኔነት እና የንስሩ ነፍስ የተሳሰረ መሆኑን ነው፡፡ የኖረውን ያህል ኖራ በሚሞትበት ቀን የምትሞት እንደሆነም ይሰማታል፡፡ወይንም የእሱ ነፍስ ከንስር አካሉ ውስጥ ተንጠፍጥበፎ በሚወጣበት ቅጽበት የእሷም ነፍስ ከዚህ የሰው ሰውነት ወይም አካል ውስጥ ተንጠፍጥፎ በመውጣት ከእሱ ነፍስ ጋር በመተቃቀፍ ወደሚሄድበት ሚስጥራዊ ቦታ አብሮት እንደሚነጉድ ታውቃለች… የመዳረሻቸው ፍጻሜም የአምላክ እቅፍ ይሆን የሉሲፈር ጓዲያ ምንም የምታውቀው ነገር የለም ፡፡
አሁን ባሉበት ቦታ ሁለቱምን ደስተኞች ናቸው ፡፡በዚህች ምድር ሚስጥር እየተደመሙበት ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ከሶስት አመት በኃላ..
እናትዬውን አሳምና ከደሎ ለቃ ስትወጣ አንድ ሻንጣ ልብሷን ይዛ በትራንስፖርት ሳይሆን በንስሯ አማካይነት እየበረረች ነበር የተጓዘችው..በእጇ እናቷ ያስጨበጠቻትን 2000 ሺ ብር እና አጎቷ የሰጣትን 5 ሺ ብር .. በቃ ይሄንን ነው የያዘችው፡፡ግን ሻንጣዋ ውስጥ ከአመታት በፊት ኪኒማጀሮን ለመጓብኘት በሄደች ጊዜ ንስሯ ከባህር ወንበዴዎች ነጥቆ የሰጣት ዳይመንድ እንደቀልድ እንዳስቀመጠችው ስለነበረ ይዛው ነበር.። አዲስ አበባ እንደገቡ በደላላ 45 ሚሊዬን ብር ተሸጠ.
በ25 ሚሊዬን ብር ለገጣፎ ከተማ አካባቢ ምታርፍበት የራሷ የሆነ 2ሺ ካ.ሬ ሜትር ግቢ ላይ ጥጉን ይዞ የታነፀ ባለአምስት ክፍል ቢላ ቤት ገዝታ ከንስሯ ጋር የብቸኝነት ኑሮ መኖር ጀመረች፡፡
እንደመጣች ሰሞን ብቸኝነቱ በጣም ከብዷት ነበር.. የምታውቀው ሰው በዙያዋ ካለመኖሩም በተጨማሪ ከደንና ጫካ ውስጥ ወጥቶ በፎቅና በመኪና የታጠረ አካባቢ መኖር በጣም ሚረብሽ ሆኖባት ነበር…ቆይቶ ግን እየለመደችው መጣች፡የገዛችውንም ጊቢ እንደምትፈልገው አደረገችው….እነሆ አሁን ከሶስት አመት በኃላ ከቤቱ ይልቅ በግቢ ውስጥ ያሉ ዛፎች ዕጻዋቶች እና ፍራፍሬዎች ይበልጥ ያስደምማሉ፡፡ በግቢዋ ውስጥ ከ1140 በላይ የዕፅዋት አይነቶች ይገኛሉ፡፡ከነዚህ ውስጥ 83ቱን ከተለያዩ አህጉራት በዞረችባቸው ወቅት ቀልቧን ስበውት ወይም አስደምመዋት አምጥታ የተከለቻቸው ናቸው፡፡እርግጥ አምጥታ የተከለቻቸው ከዚህ አሁን ከተጠቀሰው ቁጥር በሶስት እጥፍ ከፍ ያለ ነበር..ከአዲስ አበባ የአየር ፀባይ ጋር ተላምደው መጽደቅ የቻሉት ግን እነዚህ ብቻ ናቸው፡፡
ግቢዋ ውስጥ ያሉ ዕጽዋቶች ሁሉ አስደማሚነታቸው ለአይን መስብ ከመሆናቸው እና ንጽህ አየር ሚያመርቱ መንፈሳዊ ማሽኖች ስለሆኑ ብቻ አይደለም እዚህ ግቢ የመትከል ተተክሎም የመብቀል እድል ያገኙት…እያንዳንዱ የተለየ ሚስጥር እና ጥበብ የሚገለጽባቸው የእግዚያብሄርን ሚስጥራዊ ሹክሹክታ በቅጠሎቻቸው እና በስሮቻቸው ነስለሚተነፍሱ ነው…::መድሀኒት ናቸው… ታአምራትን የሚሰራባቸው ናቸው..ብዙ ብዙ ነገር…በየዛፎች ቅርንጫፍች ላይ ቁጥራቸውን የማይታወቅ የወፍ ጎጆዎች ሞልተውባቸዋል፤ሶስት ጉሬዛ እና አራት ዝንጀሮዎችም አሏት ..ሁሉንም ያመጣቻው ከሀገሯ ጫካ ነው… ከደሎ መና፡፡እንደዛ ያደረገችው..ልጅነቷን ስለሚያስታውሷት ነው.እንደዛ ያደረገችው..አብራቸው እነሱን እያየች ከእነሱ እየተጫወተች ስላደገች ዘመዷቾ ስለሚመስሏት ነው… ስለምትወዳቸውና ከእነሱ ውጭ ህይወት ስለማይታያት ነው.. ስለምትወዳቸውና የሚወዷትም ስለሚመስላት ነው፡፡
አብረዋት የሚኖሩ አንድ የስልሳ ሁለት አመት አዛውንት ሰውዬ አሉ፡፡ጋሽ ተክለወልድ ይማም ይባላሉ፡፡ይሄንን ጊቢ እንዲህ ያሳመረችውም የምታስተዳድረውም ከእሳቸው ጋር ነው፡፡
እሷ ያው አብዝታ ከአንድ የምድር ጫፍ ወደሌላው መስፈንጠር የዘወትር ድርጊቷ ስለሆነ በሌለችበት ጊዜ እሳቸው ናቸው ሙሉ ሀላፊነቱን የሚወስዱላት፡፡ ዘበኛ ወይም አትክልተኛ አይደሉም፡፡ከዕጽዋቶች ጋር በፍቅር የወደቁ ከሀለማያ ዩኒቨርሲቲ ለ32 ዓመት ያስተማሩና በቅርቡ ጡረታ የወጡ የዕጽዋት ሳይንስ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡
ሌላው በዋናነት ለብቸኝነቷ መድሀኒት የሆናት ንስሯ ነው ፡፡ የንስሯ እና የእሷ ግንኙነት ለሌላ ሰው ለማስረዳት ቀላል መንገድ የለም፡፡ እያንዳንዱ የሰው ልጅ እንዲጠብቀው እንዲንከባከበው እና ከክፉ ነገር እንዲከልለው ከፈጣሪው የተመደበለት ጠባቂ መልዐክ አለው ተብሎ በአብዛኛው ሰው ይታመናል፡፡ግን እነዚህ ጠባቂ መላዕክቶች አካል አልባ መንፈስ ናቸው ፡፡አይታዩም፤መታየት ብቻ ሳይሆን አብዛኛው ሰውም ጠባቂ መልአኩን በትከሻው ላይ ተሸክሞ እንደሚዞር አያውቅም… አያምንምም፡፡ስለዚህ አይገለገልባቸውም …አያዳምጣቸውም፡፡ሰው በጨለማ ውስጥ ሲጓዝ ማጅራት መቺ ከኃላው ካለ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ሳይሰማ ትከሻዬን ከበደኝ ይላል፤ያ ምን ማለት ነው? ለሚያምንበት ሰው ጠባቂ መላዕክ የማስጠንቂያ ደውል ነው…. እሱ ያልተመለከተውን በጭለማ ውስጥ የተሸሸገውን አጥቂውን ጠባቂ መልአኩ አይቶት ሹክ ብሎታል ማለት ነው፡፡እንግዲህ ያ ሰው ብልህ ከሆነ ማድረግ ያለበት መልዕክቱን አምኖ ተፈትልኮ በመሮጥ ማምለጥ ወይም ጥቃቱን ለመመከት እራሱን ማዘጋጀት ነው፡፡አይ ዝም ብሎ ተራ ፍራቻ ነው ብሎ የደረሰውን መልዕክት ችላ ብሎ በእንዝላልነቱ ከገፋበት ግን ማጃራቱን ተመቶ ይዘረራልም..ይዘረፋልም ማለት ሊሆን ይችላል፡፡
እና ለእሷ ይሄ ንስር አሞራ ጠባቂ መላዕኳ በሉት፡፡በአካል አብሯት የሚንቀሳቀስ የሚያወራት የምታወራው ጠባቂ መልአክ ስላለት፡፡የፈለገችበት የአለም ጥግ አንጠልጥሎ የሚወስዳት...ከሚንቀለቀል እቶን እሳት ውስጥ ብትገባ እንኳን አንጠልጥሎ በማውጣት ሀይቅ ውስጥ ጨምሮ የሚያቀዘቅዘት፡፡ካለሀሪ በረሀ ላይ ወስዶ በጥም ጉሮሮዋ ከደረቀ ከመንቁሩ ወይን አመንጭቶ የሚያጠጣት…..ከፈለገች የሲ.አይ .ኤን የስለላ መረብ በጣጥሶ የዋይት ሀውስ ራት ግብዝ ላይ አስገብቶ የሚጥላት፡፡ሱፐር ሂዩማን እንድትሆን ሱፐር ሆኖ ሱፐር የሚያደርጋት መልዐኳ ነው፡፡የማታውቀው አባቷ ስጦታ፡ከሀገሯ አብሮት የተሰደ የደስታዋም ሆነ የሀዘኗ ጊዜ ተጋሪዋ፡፡
በንስራ አካል ውስጥ ባለው የነቃና የበቃ ነፍስ እገዛ እሱ ያየውን አንደምታይ እና ያሰበውን እንዳምታስብ ታውቃለች፡፡ልክ በአንድ ዲኮደር እንደሚሰራ ሁለት ቴሌቪዝን በሉን….እሷ ቤቷ ቁጭ ብላ እሱ አየሩን ሰንጥቆ በሚበርበት የምድር ጥግ ሁሉ እያየ ያለውን ነገር ጥርት ባለ ምስል በአዕምሮዋ ታያለች…የንስርን አይን ደግሞ የሚታውቅ ነው..እያንዳንዱ ንስር ቅንጣት በቀላሉ በአይኑ ሌንስ ይቀልባታል፡፡ይሄ ገለጻ ለብዙዎችን ግራ ሊያጋባ ይችላል፡፡
ይሄ መልአክ ነው ሰይጣን የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል፡፡መልአክ ከሆነ ለምን በእርግብ አካል ውስጥ አላደረም ወይንም እንደተለመደው ለምን የበግ ስጋና ቆዳ አለበሰም፡፡እሱን የሚያውቀው ይሄ እንዲሆን ያደረገው የማታውቀውና የሌላ አለም ፍጡር የሆነው አባቷ ነው፡፡ለእሷ ግን ምንም ግድም አይሰጣትም፡፡ዋናው በእርግጠኝነት የምታውቀው ነገር የእሷ እኔነት እና የንስሩ ነፍስ የተሳሰረ መሆኑን ነው፡፡ የኖረውን ያህል ኖራ በሚሞትበት ቀን የምትሞት እንደሆነም ይሰማታል፡፡ወይንም የእሱ ነፍስ ከንስር አካሉ ውስጥ ተንጠፍጥበፎ በሚወጣበት ቅጽበት የእሷም ነፍስ ከዚህ የሰው ሰውነት ወይም አካል ውስጥ ተንጠፍጥፎ በመውጣት ከእሱ ነፍስ ጋር በመተቃቀፍ ወደሚሄድበት ሚስጥራዊ ቦታ አብሮት እንደሚነጉድ ታውቃለች… የመዳረሻቸው ፍጻሜም የአምላክ እቅፍ ይሆን የሉሲፈር ጓዲያ ምንም የምታውቀው ነገር የለም ፡፡
አሁን ባሉበት ቦታ ሁለቱምን ደስተኞች ናቸው ፡፡በዚህች ምድር ሚስጥር እየተደመሙበት ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
👍140👏13❤10😁9👎2🥰1😢1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ኬድሮን ከዕንቅልፋ የነቃችው 11 ሰዓት አካበቢ ቢሆንም መኝታ ቤቷን ለቃ ወደ በረንዳው የወጣችው 12 ሰዓት ተኩል ካለፈ በኋላ ነው፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ዘወትር እንደምታደርገው ዮጋ እየሰራች ነበር የቆየችው፡፡እቤቷን ለቃ ስትወጣ ንስሯ ተከትሏት ወጣ፡፡እሷ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ ማንበቧን ጀመረች ፡፡
ከ12 ሰዓት እስከሁለት ሰዓት ያለው ጊዜ ግቤዋ ውስጥ ባሉት ዛፎች ላይ የሰፈሩትን የተለያ አይነት የወፎች ህብረ ዝማሬ እየሰማች ንፁህ በሆነ አዕምሮዋ ተረጋግታ በተመስጦ የምታነብበት ሰዓት ነው፡፡ከሀገሯ ወጥታ ለገጣፎ ከከተመች በኃላ ያዳበረችው አዲስ ልምድ ንባብ ነው፡፡ከመፅሀፍቶች ጋር ያላት ቁርኝት ለእሷም ለራሷ እስኪገርማት ድረስ በጣም የጠነከረ ሆኗል፡፡በአጠቃላይ ሱሰኛ ሆናለች ፡፡
አንድ ሰዓት አካባቢ ከእሷ መኝታ ቤት ጎን ያለው የፕሮፌሰሩ በራፍ ተከፈተ ፡፡ያልጠበቀችው ክስተት ነበር፡፡ምክንያቱም ደግሞ የፕሮፌሰሩ ባህሪ ከእሷ የተለየ ስለሆነ ነው፡፡እሳቸው እሰከ ለሊቱ አስር ሰዓት ድረስ ይቆዩና የተለየ ፕሮግራም ከሌላቸው በስተቀር እስከ ጥዋቱ አራት ሰዓት ድረስ ይተኛሉ፡፡እና ስታነብ የነበረውን መጻሀፏን አጠፍ አድርጋ አይኗን ወደፕሮፌሰሩ በራፍ ላከች፡፡ከክፍሉ የወጡት ፕሮፌሰሩ ሳይሆኑ አንድ የ20 ዓመት አካባቢ ሚሆናት መልከ መልካም ሴት ነች፡፡ፈገግ አለች ፡፡
እኚ ሽማጊሌው ሙሁር ከአልማዝ የጠነከረ ጽናት እና የሚያስገርም ስብዕና ቢኖራቸውም ሴት ላይ ያላቸው አመል ግን የተለየ እና የሚገርም ነው፡፡ካሉበት ዕድሜ ጋር የሚቃረን አይነት ነው፡፡እሳቸው ግን ይሄንን ድክመታቸውን እንደድክመት ተመልክተውት አያውቁም፡፡ ለጤነኝነቴ እና በዚህ ዕድሜዬ ላይ ላለኝ ጥንካሬ ሚስጥሩ ሁለት ነው ፤የመጀመሪያው ከእጽዋት ጋር ያለኝ ፍቅር እና ቁርኝት ሲሆን ሌላው ደግሞ ለወሲብ ያለኝ ፍቅር ነው ብለው በድፍረት ለጠየቃቸው ሁሉ ይመልሳሉ፡፡ ጫን ብለው ለጠየቃቸውም ስለወሲብ ጥሩነት ዘርዘር አድርገው ለማስረዳት ይገደዳሉ‹‹…. የወሲብ ብቃት ቀጥታ ከጤነኝነት ጋር ትስስር አለው፣አንድ የወሲብ ብልቱ አልታዘዝ ያለው ሰው የሆነ የጓደለው ነገር አለው ማለት ነው፡፡ብዙ ጊዜ ትልቅ ቢዝነስ ሚያንቀሳሰቅሱ ባለሀብቶች ወይም ትልቅ ድርጅት ሚያሰተዳድሩ የስራ መሪዎች የወሲብ ስሜታቸው ሚቀሰቀሰው ከእለታቶች በአንድ ቀን ፤ለዛውም በብዙ ድካምና የመድሀኒት እገዛ ነው ፡፡ይህ የሚሆነበት ዋናው ምክንያት በጭንቀት የተበረዘ አዕምሮ እና በስራ የዛለ አካል ስላላቸው ነው ለወሲብ ዝግጁ መሆን የማይችሉት:: አልያም ድባቴ ውስጥ ገብተው በጭንቀት በሽታ እየተሰቃዩ ነው፡፡
ጥናተቶች አንደሚያመለክቱት የአንድ ሰው ብልቱ ሲቆም ያለው ጥንካሬ እና የልብ ጥንካሬ ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው…ተገትሮ የሚሰነጥቅ ብልት ያለው ወንድ ልቡም እንደዛው የተደራረበ ጠንካራና ከብረት የደደረ ነው፡፡ በሳምንት 4 ቀን ወሲብ የሚፈጽም ሰው ከማይፈጽም ሰው በልብ ድካም የመያዝ ዕድሉ 58 ፐርሰንት የበለጠ የተሻለ ነው ፡፡…..››እያሉ መሰል መረጃዎችን በመደርደር ያስረዳሉ፡፡
ስለእሳቸው ማሰቧን ገታ አድርጋ ፊት ለፊቷ ወዳለችው ልጅ ትኩረቷን መለሰች፡፡በዛ ተመሳሳይ ሰዓትም ንስሯ ፡፡ ከተቀመጠችበት ወንበር ትክክል ጣራው ላይ ሰፍሮ ዘና ብሎ ቁልቁል እሷንም ጊቢውንም እየቃኘ እና የጥዋቷን ፀሀይ አብሯት እየሞቀ እና የምትመለከታትን ልጅ እየተመለከተ ነው፡፡
ልጅቷ በራፉን መልሳ ዘጋችና ወደውጨኛው በራፍ ለመሄድ እርምጃ ስትጀምር አዕምሮዋን ሰረሰራት፡፡ቀና ብላ ወደ ንስሯ ስታይ እነዛ ሰርሰሪ አይኖቹን ልጅቷ ላይ ሰክቷል…‹‹ ነገር አለ›› አለችና እሷም ትኩረቷን በመሰብሰብ የሚያየየውን ለማየት ሞከረች…. የልጅቷ ልብ ጭልም ብሎ ነው እየታያት ያለው‹‹‹ ..በሀዘን ኩምትርትር ያለ….ደግሞ ግራ የተጋባ የተመሰቃቀለ ነፍስ ነው ያላቻት ›ስትለ አጉረመረመች.. ..ወጣቷ ቆንጆ ለሚያያት ሁሉ በፈገግታ የደመቀ ፊት ስለሚታየው በጨለማ የተሞላች ነፍስ አላት ተብሎ ቢነገረው ማንም አያምንም ፡፡
‹‹የእኔ እህት ››ብላ ጠራቻት
‹‹አቤት››አለችና ባለችበት ቆማ ፊቷን ወደ እሷ አዞረች…
‹‹ደህና አደርሽ …?››
‹‹ደህና ››አለች ግራ በመጋባት
‹‹ምነው በለሊት…?››
በንግግሯ ግራ ተጋብታ በእጇ የያዘችውን ሞባይል አብርታ አየችና‹‹እንድ ሰዓት እኮ ሆኗል…?››አለቻት፡፡
‹‹ካልቸኮልሽ ቁርስ አብረን እንብላና ትሄጄያለሽ›› …..ይህን ስትላት ልጅቱ እንደማትቸኩል እርግጠኛ ነኝ ….በቃ እንደውም የምትሄድበትም ያላት አይነት እንዳልሆነች ተረድታለች፡፡
እንደማቅማማት አለችና ፊቷን አዙራ ወደእሷ መጣች፤እንደዛ ያደረገችው ዝም ብላ አይደለም ….ውስጧ እንደዛ እንዳታደርግ ስለገፋፋት ነው…. ሁሌ ፕሮፌሰሩ የሚያመጧቸውን ሴቶች ወደ ክፍሏ በማስገባት ቁርስ እያበላች ትሸኛቸዋለች ማለት አይደለም፡፡በዛ ላይ እኮ ገና ቁርስም አልሰራችም፡፡ብቻ ይዛት ገባችና ቁጭ እንድትል ነገረቻት ..ያመለከተቻት ቦታ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ይቅርታ ቁርሱ አልተሰራም …ግን በፍጥነት ይደርሳል፡፡››ብላ እስቶቩን ለኮሰች
‹‹አረ ችግር የለም…››
ወደ ፊሪጅ አመራችና ከፍታ አንድ ብርጭቆ የማንጎ ጂውስ ሰጠቻት…… አመስግና ተቀበለቻትና መጠጣት ጀመረች ….እሷም እያወራቻት ቁርሱን መስራት ጀመረች…
‹‹እኔ ሶፊያ እባላለሁ…አንቺስ
…?››ሶፊያ የሚለውን ስም ለገጣፎ ከተመች ቡኃላ ደጋጋማ መጠቀም ጀምራለች፡፡ምንያቱም ከአዲስ ሰው ጋር ሁሉ ስትተዋወቅ ኬድሮን እባላለው ስትል‹‹ ኬድሮን ማለት ምን ማለት ነው?›› ብለው ሲጠየቋት እንዴት ብላ እንደምታስረዳ ግራ እየገባት ስለተቸገረች ነው፡ኬድሮን ማለት በማርስና በመሬት መካከል የሚገኝ ፕላኔት ነው ፤አባቴ የዛ ፕላኔት ኑዋሪ ነው…ትርጉሙ የዕውቀት ምድር ማለት ነው .እሱን ለማስታወስ ስትል እናቴ በፕላኔቷ ስም ስሜን ኬዴርን ብላ ሰየመችኝ ብላ ብታስረዳ‹‹እንዴ ኬድሮን የሚባል ፐላኔት መቼ ነው የተገኘው? ብለው ወደጎግል ይሮጣሉ… ምንም ሚጎለጎል መረጃ ሲያጡ እሷን እንደ እብድ ይመለከታቷል …ይሄ ነገር ሲደጋገምባት ሰለቻትና ለምን ሁለተኛ ስሜን አልጠቀምም አለችና ‹ሶፊያ› የሚል ስሞን አብዝታ መገልገል ጀመረች ፤እና ሁለቱንም ስሞቾን እንደአስፈላጊነቱ እየቀያየረች መጠቀም ጀመረች፡
‹‹አለም››
‹‹እሺ አለም….. አይዞሽ..ነገሮች ይስተካከላሉ››አለቻት፡፡
‹‹ ፍጥጥ ብላ አየቻት፡፡ምክንያቱም ስለታሪኳ ምንም አልነገረቻትም፡፡ እንዴት ልታውቅ ቻለች፤ ብላ ግራ ተጋብታ ነው፡፡››
‹‹አልገባኝም ››አለቻት፡፡
‹‹አይ አሁን ያለሽበት ችግር ይፈታል ማለቴ ነው››
በፍራቻም በጥርጣሬም እያየቻት ‹‹ነገርኩሽ እንዴ…? ››ጠየቀቻት …
‹‹አይ እንዲሁ ሳይሽ ውስጥሽ የተጨነቀ እንደሆነ ስለገባኝ ነው፡፡በጣም አዝነሻል፡፡››
እንባዋን መገደብ አቅቷት ዘረገፈችው፡፡
‹‹አዎ ከባድ ሀዘን ላይ ነኝ ፡፡››
‹‹አይዞሽ..እስኪ ንገሪኝ››
‹‹እንደምታስቢው ሸርሙጣ አይደለሁም…ይሄንን ስራ ከጀመርኩ ሳምንትም አይሆነኝም…››
‹‹አይዞሽ ..ተረጋጊና አጫውቺኝ››
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ኬድሮን ከዕንቅልፋ የነቃችው 11 ሰዓት አካበቢ ቢሆንም መኝታ ቤቷን ለቃ ወደ በረንዳው የወጣችው 12 ሰዓት ተኩል ካለፈ በኋላ ነው፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ዘወትር እንደምታደርገው ዮጋ እየሰራች ነበር የቆየችው፡፡እቤቷን ለቃ ስትወጣ ንስሯ ተከትሏት ወጣ፡፡እሷ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ ማንበቧን ጀመረች ፡፡
ከ12 ሰዓት እስከሁለት ሰዓት ያለው ጊዜ ግቤዋ ውስጥ ባሉት ዛፎች ላይ የሰፈሩትን የተለያ አይነት የወፎች ህብረ ዝማሬ እየሰማች ንፁህ በሆነ አዕምሮዋ ተረጋግታ በተመስጦ የምታነብበት ሰዓት ነው፡፡ከሀገሯ ወጥታ ለገጣፎ ከከተመች በኃላ ያዳበረችው አዲስ ልምድ ንባብ ነው፡፡ከመፅሀፍቶች ጋር ያላት ቁርኝት ለእሷም ለራሷ እስኪገርማት ድረስ በጣም የጠነከረ ሆኗል፡፡በአጠቃላይ ሱሰኛ ሆናለች ፡፡
አንድ ሰዓት አካባቢ ከእሷ መኝታ ቤት ጎን ያለው የፕሮፌሰሩ በራፍ ተከፈተ ፡፡ያልጠበቀችው ክስተት ነበር፡፡ምክንያቱም ደግሞ የፕሮፌሰሩ ባህሪ ከእሷ የተለየ ስለሆነ ነው፡፡እሳቸው እሰከ ለሊቱ አስር ሰዓት ድረስ ይቆዩና የተለየ ፕሮግራም ከሌላቸው በስተቀር እስከ ጥዋቱ አራት ሰዓት ድረስ ይተኛሉ፡፡እና ስታነብ የነበረውን መጻሀፏን አጠፍ አድርጋ አይኗን ወደፕሮፌሰሩ በራፍ ላከች፡፡ከክፍሉ የወጡት ፕሮፌሰሩ ሳይሆኑ አንድ የ20 ዓመት አካባቢ ሚሆናት መልከ መልካም ሴት ነች፡፡ፈገግ አለች ፡፡
እኚ ሽማጊሌው ሙሁር ከአልማዝ የጠነከረ ጽናት እና የሚያስገርም ስብዕና ቢኖራቸውም ሴት ላይ ያላቸው አመል ግን የተለየ እና የሚገርም ነው፡፡ካሉበት ዕድሜ ጋር የሚቃረን አይነት ነው፡፡እሳቸው ግን ይሄንን ድክመታቸውን እንደድክመት ተመልክተውት አያውቁም፡፡ ለጤነኝነቴ እና በዚህ ዕድሜዬ ላይ ላለኝ ጥንካሬ ሚስጥሩ ሁለት ነው ፤የመጀመሪያው ከእጽዋት ጋር ያለኝ ፍቅር እና ቁርኝት ሲሆን ሌላው ደግሞ ለወሲብ ያለኝ ፍቅር ነው ብለው በድፍረት ለጠየቃቸው ሁሉ ይመልሳሉ፡፡ ጫን ብለው ለጠየቃቸውም ስለወሲብ ጥሩነት ዘርዘር አድርገው ለማስረዳት ይገደዳሉ‹‹…. የወሲብ ብቃት ቀጥታ ከጤነኝነት ጋር ትስስር አለው፣አንድ የወሲብ ብልቱ አልታዘዝ ያለው ሰው የሆነ የጓደለው ነገር አለው ማለት ነው፡፡ብዙ ጊዜ ትልቅ ቢዝነስ ሚያንቀሳሰቅሱ ባለሀብቶች ወይም ትልቅ ድርጅት ሚያሰተዳድሩ የስራ መሪዎች የወሲብ ስሜታቸው ሚቀሰቀሰው ከእለታቶች በአንድ ቀን ፤ለዛውም በብዙ ድካምና የመድሀኒት እገዛ ነው ፡፡ይህ የሚሆነበት ዋናው ምክንያት በጭንቀት የተበረዘ አዕምሮ እና በስራ የዛለ አካል ስላላቸው ነው ለወሲብ ዝግጁ መሆን የማይችሉት:: አልያም ድባቴ ውስጥ ገብተው በጭንቀት በሽታ እየተሰቃዩ ነው፡፡
ጥናተቶች አንደሚያመለክቱት የአንድ ሰው ብልቱ ሲቆም ያለው ጥንካሬ እና የልብ ጥንካሬ ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው…ተገትሮ የሚሰነጥቅ ብልት ያለው ወንድ ልቡም እንደዛው የተደራረበ ጠንካራና ከብረት የደደረ ነው፡፡ በሳምንት 4 ቀን ወሲብ የሚፈጽም ሰው ከማይፈጽም ሰው በልብ ድካም የመያዝ ዕድሉ 58 ፐርሰንት የበለጠ የተሻለ ነው ፡፡…..››እያሉ መሰል መረጃዎችን በመደርደር ያስረዳሉ፡፡
ስለእሳቸው ማሰቧን ገታ አድርጋ ፊት ለፊቷ ወዳለችው ልጅ ትኩረቷን መለሰች፡፡በዛ ተመሳሳይ ሰዓትም ንስሯ ፡፡ ከተቀመጠችበት ወንበር ትክክል ጣራው ላይ ሰፍሮ ዘና ብሎ ቁልቁል እሷንም ጊቢውንም እየቃኘ እና የጥዋቷን ፀሀይ አብሯት እየሞቀ እና የምትመለከታትን ልጅ እየተመለከተ ነው፡፡
ልጅቷ በራፉን መልሳ ዘጋችና ወደውጨኛው በራፍ ለመሄድ እርምጃ ስትጀምር አዕምሮዋን ሰረሰራት፡፡ቀና ብላ ወደ ንስሯ ስታይ እነዛ ሰርሰሪ አይኖቹን ልጅቷ ላይ ሰክቷል…‹‹ ነገር አለ›› አለችና እሷም ትኩረቷን በመሰብሰብ የሚያየየውን ለማየት ሞከረች…. የልጅቷ ልብ ጭልም ብሎ ነው እየታያት ያለው‹‹‹ ..በሀዘን ኩምትርትር ያለ….ደግሞ ግራ የተጋባ የተመሰቃቀለ ነፍስ ነው ያላቻት ›ስትለ አጉረመረመች.. ..ወጣቷ ቆንጆ ለሚያያት ሁሉ በፈገግታ የደመቀ ፊት ስለሚታየው በጨለማ የተሞላች ነፍስ አላት ተብሎ ቢነገረው ማንም አያምንም ፡፡
‹‹የእኔ እህት ››ብላ ጠራቻት
‹‹አቤት››አለችና ባለችበት ቆማ ፊቷን ወደ እሷ አዞረች…
‹‹ደህና አደርሽ …?››
‹‹ደህና ››አለች ግራ በመጋባት
‹‹ምነው በለሊት…?››
በንግግሯ ግራ ተጋብታ በእጇ የያዘችውን ሞባይል አብርታ አየችና‹‹እንድ ሰዓት እኮ ሆኗል…?››አለቻት፡፡
‹‹ካልቸኮልሽ ቁርስ አብረን እንብላና ትሄጄያለሽ›› …..ይህን ስትላት ልጅቱ እንደማትቸኩል እርግጠኛ ነኝ ….በቃ እንደውም የምትሄድበትም ያላት አይነት እንዳልሆነች ተረድታለች፡፡
እንደማቅማማት አለችና ፊቷን አዙራ ወደእሷ መጣች፤እንደዛ ያደረገችው ዝም ብላ አይደለም ….ውስጧ እንደዛ እንዳታደርግ ስለገፋፋት ነው…. ሁሌ ፕሮፌሰሩ የሚያመጧቸውን ሴቶች ወደ ክፍሏ በማስገባት ቁርስ እያበላች ትሸኛቸዋለች ማለት አይደለም፡፡በዛ ላይ እኮ ገና ቁርስም አልሰራችም፡፡ብቻ ይዛት ገባችና ቁጭ እንድትል ነገረቻት ..ያመለከተቻት ቦታ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ይቅርታ ቁርሱ አልተሰራም …ግን በፍጥነት ይደርሳል፡፡››ብላ እስቶቩን ለኮሰች
‹‹አረ ችግር የለም…››
ወደ ፊሪጅ አመራችና ከፍታ አንድ ብርጭቆ የማንጎ ጂውስ ሰጠቻት…… አመስግና ተቀበለቻትና መጠጣት ጀመረች ….እሷም እያወራቻት ቁርሱን መስራት ጀመረች…
‹‹እኔ ሶፊያ እባላለሁ…አንቺስ
…?››ሶፊያ የሚለውን ስም ለገጣፎ ከተመች ቡኃላ ደጋጋማ መጠቀም ጀምራለች፡፡ምንያቱም ከአዲስ ሰው ጋር ሁሉ ስትተዋወቅ ኬድሮን እባላለው ስትል‹‹ ኬድሮን ማለት ምን ማለት ነው?›› ብለው ሲጠየቋት እንዴት ብላ እንደምታስረዳ ግራ እየገባት ስለተቸገረች ነው፡ኬድሮን ማለት በማርስና በመሬት መካከል የሚገኝ ፕላኔት ነው ፤አባቴ የዛ ፕላኔት ኑዋሪ ነው…ትርጉሙ የዕውቀት ምድር ማለት ነው .እሱን ለማስታወስ ስትል እናቴ በፕላኔቷ ስም ስሜን ኬዴርን ብላ ሰየመችኝ ብላ ብታስረዳ‹‹እንዴ ኬድሮን የሚባል ፐላኔት መቼ ነው የተገኘው? ብለው ወደጎግል ይሮጣሉ… ምንም ሚጎለጎል መረጃ ሲያጡ እሷን እንደ እብድ ይመለከታቷል …ይሄ ነገር ሲደጋገምባት ሰለቻትና ለምን ሁለተኛ ስሜን አልጠቀምም አለችና ‹ሶፊያ› የሚል ስሞን አብዝታ መገልገል ጀመረች ፤እና ሁለቱንም ስሞቾን እንደአስፈላጊነቱ እየቀያየረች መጠቀም ጀመረች፡
‹‹አለም››
‹‹እሺ አለም….. አይዞሽ..ነገሮች ይስተካከላሉ››አለቻት፡፡
‹‹ ፍጥጥ ብላ አየቻት፡፡ምክንያቱም ስለታሪኳ ምንም አልነገረቻትም፡፡ እንዴት ልታውቅ ቻለች፤ ብላ ግራ ተጋብታ ነው፡፡››
‹‹አልገባኝም ››አለቻት፡፡
‹‹አይ አሁን ያለሽበት ችግር ይፈታል ማለቴ ነው››
በፍራቻም በጥርጣሬም እያየቻት ‹‹ነገርኩሽ እንዴ…? ››ጠየቀቻት …
‹‹አይ እንዲሁ ሳይሽ ውስጥሽ የተጨነቀ እንደሆነ ስለገባኝ ነው፡፡በጣም አዝነሻል፡፡››
እንባዋን መገደብ አቅቷት ዘረገፈችው፡፡
‹‹አዎ ከባድ ሀዘን ላይ ነኝ ፡፡››
‹‹አይዞሽ..እስኪ ንገሪኝ››
‹‹እንደምታስቢው ሸርሙጣ አይደለሁም…ይሄንን ስራ ከጀመርኩ ሳምንትም አይሆነኝም…››
‹‹አይዞሽ ..ተረጋጊና አጫውቺኝ››
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
✨ይቀጥላል✨
👍153❤17👏1😁1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
‹‹በባሏ ጠርጥራሽ ነው አይደል …?››ያው እኔ ሳላስበው ነው ቀደም ቀድም የምለው ….ምክንያቱም እሷ ታሪኳን በቃላት አቀናብራ ለሶፊ ከመናገሯ በፊት እሷ ቀድሞ ይታያታል…ንስሯ የበራፍ በረንዳ ላይ ሶፊ ከለቀቀችበት ወንበር ላይ ተፈናጦ ክፍት በሆነው በራፍ ወደውስጥ አጨንቁሮል ….እርግጥ ልጅቷ ጀርባውና ስለሰጠችው እስከአሁን አላየችውም… እሷ ግን ፊት ለፊት ይታያታል ሁለቱም የልጅቷን ታሪክ ላይ አተኩረዋል …ለዛ ነው ቀደም ቀደም የምትለው….ያ ደግሞ ልጅቷን ግራ እያጋባት ስለሆነ መረጋጋት እንዳለባት ለራሷ እየነገረች ነው፡፡
‹‹አዎ ትክክል ነሽ…ብታይ ጭራቅ ሴት ነች፡፡ቅናቷ አያድረስ ነው፡፡በቃ ሰይጣናዊ የቅናት ዛር ነው የሰፈረባት፡፡ኑሮዬን ሁሉ ሲኦል ነው ያደረገችው፡፡››
‹‹ሙሉውን ሶስት አመት እዛው ነው የኖርሺው…?››
‹‹አዎ ሶስት አመት ሙሉ አንድ ቤት ነበርኩ…እርግጥ መጀመሪያውን አንድ አመት አካባቢ ጥሩ ሴት ነበረች…ሁሉ ነገር መልካም ነበር… ደሞዜን በስርአቱ ትከፍለኛለች..እርግጥ እስከመጨረሻውም ደሞዜን ከልክላኝ ወይም አቋርጣብኝ አታውቅም…ለቤተሰቦቼ የምልከው ተጨማሪ ብር ሁሉ ትሰጠኝ ነበር፡፡ከዛ ድንገት ፀባይዋ ተቀያየረ….ለዓይኖቾ ተጠየፈችኝ….
‹‹ለምን ታዲያ አትለቂም ነበር..?ማለት ሌላ ማዳም ጋር ቀይረሽ መስራት ትቺይ ነበር…››
‹‹ያው እንደነገርኩሽ በህገወጥ መንገድ ነው የሄድኩት.. እንደልቤ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሼ ስራ ማማረጥ አልችልም..ሌላው …››ብላ ዝም አለች ..ላውራ ወይስ ይቅርብኝ እያለች ከራሷ ጋ ሙግት የገጠመች መሆኑን አውቃባታለች…
‹‹ሌላው ምን…?››
‹‹ሰውዬው በጣም መልካም ሰው ነው…ልጆቹንም በጣም ነው የምወዳቸው….ለእነሱ ስል ነው ታግሼያት የኖርኩት››
ፈገግ አለች‹‹መጨረሻ ታዲያ እንዴት ሆነ?››
‹‹ቅናቷ ከቁጥጥር በላይ ሆነብኛ››
‹‹ያው ምታደርጉትን እኮ ስለምታይ ነው››
‹‹ማለት…? እንዴት ታውቃለች……?›.
‹‹እርግጥ የእሷን አለመኖር እየጠበቃችሁ ነው ፍቅራችሁን የምትወጡት… ግን እሷ በደንብ ታውቃለች ..እንደውም ጥሩ ሰው ነች››አለቻት
ልጅቷ ግራ ገባት ..ከድንጋጤዋ የተነሳም ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ሁሉ ለቃ መውጣት ፈልጋለች..…
‹‹አይዞሽ አትደንግጪ …እሷን ለማስቀየም ወይም ለመበደል ብለሽ ሳይሆን ፍቅር ላይ ስለወደቅሽ ነው እንደዛ ያደረግሽው…ያ ደግሞ ከሰውዬው ቀረቤታ እና መልካምነት የተነሳ ነው..በዛ ላይ በጣም ቆንጆ እና ዘናጭ ነው…እንደምትወጂው አውቃለሁ ፡፡እሱም በደንብ ነው የሚያፈቅርሽ፡፡በጣም የከፋው ነገር ግን ቅናተኛ ላልሻት ሴት ደግሞ ሰውዬው ሁለመናዋ ነው…እናንተ እርስ በርስ ከምትዋደዱት በላይ እሷ እሱን ትወደዋለች፡፡እና ሴትዬዋ በተፈጥሮዋ መጥፎ ሆና አንቺን በማሰቃየት የምትረካ ስለሆነች ሳይሆን ባሏን ላለማጣት የምታደረግው መፋለም እና ጥረት ነበር፡፡እንደውም አንቺን ባሰቃየች ቁጥር እሱንም የምታስከፋው እና የምታጣው መስሎ ስለሚሰማት በጣም ትጨናነቅ እና ትጠነቀቅ ነበር…አንቺን ጎድታኛለች ብለሽ ከምታወሪው በላይ እሷ እራሷን አሰቃይታለች ….የጨጋራ በሽተኛ ሆናለች….››
‹‹ቆይ አንቺ ይሄን ሁሉ እንዴት ልታውቂ ቻልሽ…?››
እሱን ልታስረዳት አልቻለችም ‹‹..ትኩረት ከሰጠው አንዳንድ ነገሮችን ማየት እችላለሁ፡፡
በውስጥሽ ይህቺ ልጅ ጠንቆይ ነች እንዴ…? እያልሽ እያሰብሽ እንደሆነ አውቃለሁ..እንደዛ በይው ችግር የለውም››
‹‹አይ ማለቴ ….ልዋሽሽ አልችልም እንዳልሽው ነበር እያሰብኩ ያለሁት…ይገርማል ያልሻቸውን ብዙውን ነገሮች ትክክል ነሽ››
‹‹ምንድነው ትክክል ያልሆንኩት…?››
‹‹እሷ ስለእኛ ግንኙነት በእርግጠኝነት ማወቋን እና..ከእኔ በላይ እሱን ማፍቀሯን››
‹‹ሁለታችሁ ፍቅር የምትሰሩት አንቺ ክፍል አይደል…?››
‹‹አዎ ግን እሷ ስራ በምትሆንበት እና ከቤት እርቃ በሄደችበት ጌዜ ጠብቀንና ተጠንቅቀን ነው››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ …በሁለታችሁ ያልተለመደ መቀራረብ ጥርጣሬ ካደረባት በኃላ ግን ክፍልሽ ውስጥ በስውር ካሜራ ስላስቀመጠች የተቀዳውን በፈለገችው ጌዜ ከፍታ ታየው ነበር፡፡››
‹‹ያማ አይሆንም..…?እንዴት ተደርጎ…?››
‹‹እንደዛ ነበር የሆነው…ከእኔ በላይ አታፈቅረውም ያልሺው ደግሞ ያው በራስሽ ሚዛን ስለምትመዝኚው ነው እንደዛ የምታስቢው እንጂ እንቺ በእሷ ቦታ ብትሆኚ እርግጠኛ ነኝ ወይ ጥለሺው ትሄጂያለሽ ..ወይ ሌላ እርምጃ ትወስጂያለሽ ….እሷ ግን ካንቺ ጋር ብትጨቃጨቅም ….አንቺን ላይ ችግር ለመፍጠር ብትሞክርም አንድ ቀን እንኳን እሱ ላይ ተነጫንጫበት ወይንም ጉዳዩን አንስታበትና ወቅሳው አታውቅም..ለእሷ እሱ ብቸኛው ፍቅሯ ነው..ለአንቺ ግን የመጀመሪያ ምርጫሽ አይደለም..ስለምታፈቅሪው ብቻ ሳይሆን ማዳሞ ከምታውቀው ሌላ ተጨማሪ ብር ስለሚሰጥሽ ነው ..ፍቅርሽ ብቻ ሳይሆን የገንዘብ ምንጭሽም ስለሆነ ነው…ለእሷ ግን እንደዛ አልነበረም…››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው….የእውነት ካሜራው ኖሮ የምናደርገውን ሁሉ እያየች በትዕግስት አልፋን ከሆነ የሚገርም ነው…እኔ ብሆን ልገድለው ሁሉ እችላለሁ…አረ ሁለቱንም ነው በተቃቀፉበት የማጠፋቸው››
‹‹አየሽ..ሴትየዋ የምታስቢያትን ያህል ክፉ አልነበረችም….ከዚህም በላይ ልታሰቃይሽ ምክንያቱን ሰጥተሻት ነበር…ግን እሷ በተቻላት መጠን እራሷን ለመቆጣጠር ሞክራለች፡፡››
‹‹አዎ አንቺ ይገርማል… አሁን ሳስበው በህይወት ስላለውም እድለኛ ነኝ….››
‹‹እና እዚህ ስትመጪ ደግሞ ሌላ ታሪክ አጋጠመሽ››
‹‹አዎ በጣም የሚያንገበግበው እና ስብርብር ያደረገኝ ደግሞ ይሄኛው ነው›› አለች …..አሁን በፍራቻ እና በአድናቆት ነበር የምትመልስልኝ
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደችና ቀጠለች‹‹መቼስ ታውቂዋለሽ…አንድ ቀን ወደ ሀገሬ ስመለስ ቤት ይኖረኛል….አገባዋለሁ..ልጅ ወልድለታለሁ ብዬ ደሞዜንም .ሰውዬው ይሰጠኝ የነበረውንም ብር እልክለት ነበር…ቤት እየሰራው ነው ይለኛል….የቤት ዕቃ እያሞለው ነው ይለኛል..ምን አለፋሽ ከሶስት መቶ ሺ ብር በላይ ነው የላኩለት …..ግን ስደርስ ሌላ ሴት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዶ ጠበቀኝ…..ከዛ ምን ልንገርሽ ሁሉ ነገር አስጠላኝ …ክፍለሀገር ወደ ቤተሰቦቼም መሄድ አልፈለግኩም እንዴት ብዬ ምን ይዤ ሄዳለሁ…?……..
‹‹አዎ ለእሱ ያልሽውን ሶስት መቶ ሺብር ስትልኪለት ለቤተሰቦችሽ የላክሺው ብር ሲደመር 50 ሺ ብርም አይሞላም..››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..የሚያንገበግበኝ እና ሞራሌን እንክትክት ያደረገው እና ዛሬ እዚህ ያስገኘኝ ይሄው ነው….
አይዞሽ እናስተካክለዋለን ..በእኔ ተማመኚ..አልኳትና የደረሰውን ቁርስ አቅርቤ መብላት ጀመርን›…
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
‹‹በባሏ ጠርጥራሽ ነው አይደል …?››ያው እኔ ሳላስበው ነው ቀደም ቀድም የምለው ….ምክንያቱም እሷ ታሪኳን በቃላት አቀናብራ ለሶፊ ከመናገሯ በፊት እሷ ቀድሞ ይታያታል…ንስሯ የበራፍ በረንዳ ላይ ሶፊ ከለቀቀችበት ወንበር ላይ ተፈናጦ ክፍት በሆነው በራፍ ወደውስጥ አጨንቁሮል ….እርግጥ ልጅቷ ጀርባውና ስለሰጠችው እስከአሁን አላየችውም… እሷ ግን ፊት ለፊት ይታያታል ሁለቱም የልጅቷን ታሪክ ላይ አተኩረዋል …ለዛ ነው ቀደም ቀደም የምትለው….ያ ደግሞ ልጅቷን ግራ እያጋባት ስለሆነ መረጋጋት እንዳለባት ለራሷ እየነገረች ነው፡፡
‹‹አዎ ትክክል ነሽ…ብታይ ጭራቅ ሴት ነች፡፡ቅናቷ አያድረስ ነው፡፡በቃ ሰይጣናዊ የቅናት ዛር ነው የሰፈረባት፡፡ኑሮዬን ሁሉ ሲኦል ነው ያደረገችው፡፡››
‹‹ሙሉውን ሶስት አመት እዛው ነው የኖርሺው…?››
‹‹አዎ ሶስት አመት ሙሉ አንድ ቤት ነበርኩ…እርግጥ መጀመሪያውን አንድ አመት አካባቢ ጥሩ ሴት ነበረች…ሁሉ ነገር መልካም ነበር… ደሞዜን በስርአቱ ትከፍለኛለች..እርግጥ እስከመጨረሻውም ደሞዜን ከልክላኝ ወይም አቋርጣብኝ አታውቅም…ለቤተሰቦቼ የምልከው ተጨማሪ ብር ሁሉ ትሰጠኝ ነበር፡፡ከዛ ድንገት ፀባይዋ ተቀያየረ….ለዓይኖቾ ተጠየፈችኝ….
‹‹ለምን ታዲያ አትለቂም ነበር..?ማለት ሌላ ማዳም ጋር ቀይረሽ መስራት ትቺይ ነበር…››
‹‹ያው እንደነገርኩሽ በህገወጥ መንገድ ነው የሄድኩት.. እንደልቤ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሼ ስራ ማማረጥ አልችልም..ሌላው …››ብላ ዝም አለች ..ላውራ ወይስ ይቅርብኝ እያለች ከራሷ ጋ ሙግት የገጠመች መሆኑን አውቃባታለች…
‹‹ሌላው ምን…?››
‹‹ሰውዬው በጣም መልካም ሰው ነው…ልጆቹንም በጣም ነው የምወዳቸው….ለእነሱ ስል ነው ታግሼያት የኖርኩት››
ፈገግ አለች‹‹መጨረሻ ታዲያ እንዴት ሆነ?››
‹‹ቅናቷ ከቁጥጥር በላይ ሆነብኛ››
‹‹ያው ምታደርጉትን እኮ ስለምታይ ነው››
‹‹ማለት…? እንዴት ታውቃለች……?›.
‹‹እርግጥ የእሷን አለመኖር እየጠበቃችሁ ነው ፍቅራችሁን የምትወጡት… ግን እሷ በደንብ ታውቃለች ..እንደውም ጥሩ ሰው ነች››አለቻት
ልጅቷ ግራ ገባት ..ከድንጋጤዋ የተነሳም ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ሁሉ ለቃ መውጣት ፈልጋለች..…
‹‹አይዞሽ አትደንግጪ …እሷን ለማስቀየም ወይም ለመበደል ብለሽ ሳይሆን ፍቅር ላይ ስለወደቅሽ ነው እንደዛ ያደረግሽው…ያ ደግሞ ከሰውዬው ቀረቤታ እና መልካምነት የተነሳ ነው..በዛ ላይ በጣም ቆንጆ እና ዘናጭ ነው…እንደምትወጂው አውቃለሁ ፡፡እሱም በደንብ ነው የሚያፈቅርሽ፡፡በጣም የከፋው ነገር ግን ቅናተኛ ላልሻት ሴት ደግሞ ሰውዬው ሁለመናዋ ነው…እናንተ እርስ በርስ ከምትዋደዱት በላይ እሷ እሱን ትወደዋለች፡፡እና ሴትዬዋ በተፈጥሮዋ መጥፎ ሆና አንቺን በማሰቃየት የምትረካ ስለሆነች ሳይሆን ባሏን ላለማጣት የምታደረግው መፋለም እና ጥረት ነበር፡፡እንደውም አንቺን ባሰቃየች ቁጥር እሱንም የምታስከፋው እና የምታጣው መስሎ ስለሚሰማት በጣም ትጨናነቅ እና ትጠነቀቅ ነበር…አንቺን ጎድታኛለች ብለሽ ከምታወሪው በላይ እሷ እራሷን አሰቃይታለች ….የጨጋራ በሽተኛ ሆናለች….››
‹‹ቆይ አንቺ ይሄን ሁሉ እንዴት ልታውቂ ቻልሽ…?››
እሱን ልታስረዳት አልቻለችም ‹‹..ትኩረት ከሰጠው አንዳንድ ነገሮችን ማየት እችላለሁ፡፡
በውስጥሽ ይህቺ ልጅ ጠንቆይ ነች እንዴ…? እያልሽ እያሰብሽ እንደሆነ አውቃለሁ..እንደዛ በይው ችግር የለውም››
‹‹አይ ማለቴ ….ልዋሽሽ አልችልም እንዳልሽው ነበር እያሰብኩ ያለሁት…ይገርማል ያልሻቸውን ብዙውን ነገሮች ትክክል ነሽ››
‹‹ምንድነው ትክክል ያልሆንኩት…?››
‹‹እሷ ስለእኛ ግንኙነት በእርግጠኝነት ማወቋን እና..ከእኔ በላይ እሱን ማፍቀሯን››
‹‹ሁለታችሁ ፍቅር የምትሰሩት አንቺ ክፍል አይደል…?››
‹‹አዎ ግን እሷ ስራ በምትሆንበት እና ከቤት እርቃ በሄደችበት ጌዜ ጠብቀንና ተጠንቅቀን ነው››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ …በሁለታችሁ ያልተለመደ መቀራረብ ጥርጣሬ ካደረባት በኃላ ግን ክፍልሽ ውስጥ በስውር ካሜራ ስላስቀመጠች የተቀዳውን በፈለገችው ጌዜ ከፍታ ታየው ነበር፡፡››
‹‹ያማ አይሆንም..…?እንዴት ተደርጎ…?››
‹‹እንደዛ ነበር የሆነው…ከእኔ በላይ አታፈቅረውም ያልሺው ደግሞ ያው በራስሽ ሚዛን ስለምትመዝኚው ነው እንደዛ የምታስቢው እንጂ እንቺ በእሷ ቦታ ብትሆኚ እርግጠኛ ነኝ ወይ ጥለሺው ትሄጂያለሽ ..ወይ ሌላ እርምጃ ትወስጂያለሽ ….እሷ ግን ካንቺ ጋር ብትጨቃጨቅም ….አንቺን ላይ ችግር ለመፍጠር ብትሞክርም አንድ ቀን እንኳን እሱ ላይ ተነጫንጫበት ወይንም ጉዳዩን አንስታበትና ወቅሳው አታውቅም..ለእሷ እሱ ብቸኛው ፍቅሯ ነው..ለአንቺ ግን የመጀመሪያ ምርጫሽ አይደለም..ስለምታፈቅሪው ብቻ ሳይሆን ማዳሞ ከምታውቀው ሌላ ተጨማሪ ብር ስለሚሰጥሽ ነው ..ፍቅርሽ ብቻ ሳይሆን የገንዘብ ምንጭሽም ስለሆነ ነው…ለእሷ ግን እንደዛ አልነበረም…››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው….የእውነት ካሜራው ኖሮ የምናደርገውን ሁሉ እያየች በትዕግስት አልፋን ከሆነ የሚገርም ነው…እኔ ብሆን ልገድለው ሁሉ እችላለሁ…አረ ሁለቱንም ነው በተቃቀፉበት የማጠፋቸው››
‹‹አየሽ..ሴትየዋ የምታስቢያትን ያህል ክፉ አልነበረችም….ከዚህም በላይ ልታሰቃይሽ ምክንያቱን ሰጥተሻት ነበር…ግን እሷ በተቻላት መጠን እራሷን ለመቆጣጠር ሞክራለች፡፡››
‹‹አዎ አንቺ ይገርማል… አሁን ሳስበው በህይወት ስላለውም እድለኛ ነኝ….››
‹‹እና እዚህ ስትመጪ ደግሞ ሌላ ታሪክ አጋጠመሽ››
‹‹አዎ በጣም የሚያንገበግበው እና ስብርብር ያደረገኝ ደግሞ ይሄኛው ነው›› አለች …..አሁን በፍራቻ እና በአድናቆት ነበር የምትመልስልኝ
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደችና ቀጠለች‹‹መቼስ ታውቂዋለሽ…አንድ ቀን ወደ ሀገሬ ስመለስ ቤት ይኖረኛል….አገባዋለሁ..ልጅ ወልድለታለሁ ብዬ ደሞዜንም .ሰውዬው ይሰጠኝ የነበረውንም ብር እልክለት ነበር…ቤት እየሰራው ነው ይለኛል….የቤት ዕቃ እያሞለው ነው ይለኛል..ምን አለፋሽ ከሶስት መቶ ሺ ብር በላይ ነው የላኩለት …..ግን ስደርስ ሌላ ሴት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዶ ጠበቀኝ…..ከዛ ምን ልንገርሽ ሁሉ ነገር አስጠላኝ …ክፍለሀገር ወደ ቤተሰቦቼም መሄድ አልፈለግኩም እንዴት ብዬ ምን ይዤ ሄዳለሁ…?……..
‹‹አዎ ለእሱ ያልሽውን ሶስት መቶ ሺብር ስትልኪለት ለቤተሰቦችሽ የላክሺው ብር ሲደመር 50 ሺ ብርም አይሞላም..››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ..የሚያንገበግበኝ እና ሞራሌን እንክትክት ያደረገው እና ዛሬ እዚህ ያስገኘኝ ይሄው ነው….
አይዞሽ እናስተካክለዋለን ..በእኔ ተማመኚ..አልኳትና የደረሰውን ቁርስ አቅርቤ መብላት ጀመርን›…
✨ይቀጥላል✨
👍126❤20😁5👎3👏2😱2🔥1😢1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ከልጅቷ ጋር ሲያወሩ እና ከቤት ሲወጡ ሶስት ሰዓት ሆነ….‹‹ፍቅረኛሽ አሁን የት ነው የሚኖረው?፡፡››ጠየቀቻት፡፡
‹‹እዚሁ አዲስ አበባ ቤቴል አካባቢ እቤተሰቦቹ ያወረሱት ቤት ውስጥ ነው የሚኖረው፡፡››
‹‹ፎቶው አለሽ?››
‹‹አዎ›› ብላት ሞባይሏን ከፈተችና አሳየቻት፡፡ሞባይሏን ተቀብላ ተመለከተችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ‹‹ተከተይኝ ››አለቻት እና ወደበረንዳው ወጡ…ንስሯ ተረጋግቶ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ስታየው እንደመፍራትም ግራ እንደመጋባትም አለችና፡፡
‹‹ምን አይነት አሞራ ነው..አይፈራም እንዴ? ››
‹‹የእኔ ነው››
‹‹አሞራው?››
‹‹አዎ…ግን አሞራ ሳይሆን ንስር ነው…የእኔ ንሰር ፡፡››
‹‹ምን ያደርግልሻል?፡፡››
‹‹እሱማ ለእኔ ብዙ ነገሬ ነው… የፈለኩትን ነገር ያደርግልኛል..እኔ እንደውም የሚገርመኝ እኔ ለእሱ ምን አደርግለታለሁ ሚለውን ነው››
‹‹ይቅርታ ግን ያስፈራል…. .በተለይ አይኖቹ እና መንቁሩ…››እሷን ችላ አለቻትና ሞባይሏ ላይ ያለውን የልጅቷን ፍቅረኛ ፎቶ ለንስሯ እያሳየች ‹‹….እንርዳት መሰለኝ…እወነቱን ማወቅ መብት አላት››ስትለው ክንፎቹን አርገፈገፈና መቀመጫውን ለቆ በአየር ላይ ተንሳፈፈ…እሷ በርግጋ ወደኃላዋ አፈገፈገች….ወደላይ ተምዘግዝጎ አየሩን እየሰነጠቀ ከፍታውን ለአይን መታየት እሰከማይችል ድረስ ርቆ ተሰወረ፡
‹‹ቁጭ በይ› አለቻትና በረንዳው ላይ ካለው ወንበር አንዱን እያሳየቻት እሷ ንስሯ በለቀቀላት ወንበር ላይ እየተቀመጠች፡፡
‹‹ሄደብሽ እኮ …እንዲህ እርቆ ሄዶ አሁን አውቆ ተመልሶ ይመጣል?፡፡››
‹‹አዎ የእኔ እወቀት ዘጠና ፐርሰንቱ ከእሱ የማገኘው ነው…ንስሮች በተፈጥሮቸው በጣም ልዩ የሆኑ የአእዋፋት ዝርያዎች ናቸው፡፡እይታቸውም ጥልቅ አስተሳሰባቸውም ስል እና የተሞረደ ነው፡፡ከዛም በላይ ግን የእኔ ንስር የተለየ ነው፡፡እንዴት የሚለውን ነገር ላብራራልሽ አልችልም..ግን አሁን የሚያደርገውን ታያለሽ ..ከዛ እራስሽ ትፈርጂያለሽ››
‹‹እንዴት?››
‹‹አሁን ፍቅረኛሽን ፎቶ እያሳየሁት ሳወራው አላየሽም?››
‹‹አይቻለው.ግን እናቴም ሲጨንቃት እና በሆዷ ነገር ሲገባ ከምታልባት ላም ጋር ታወራ ነበር…እንደውም ለእሱ ስታወሪ እናቴ ነች ትዝ ያለችኝ፡፡››
‹‹አይ ይሄ ይለያል..አሁን ያንችን ችግር ማለት ስለፍቅረኛሽ ትክክለኛ ነገር እንዲያጣራልኝ ነው የላኩት››
‹‹እንዲት አድርጎ››
‹‹በቃ የተለየ ችሎታ አለው… ማንኛውም ነገር ካተኮረበት የውስጡን ሀሳብ እና ጠቅላላ ታሪኩን ማንበብ ይችላል…እኔ ደግሞ ከሱ አዕምሮ ማንበብ እችላለሁ..ወይም እንዳውቀው አዕምሮውን ይከፍትልኛል..ቅድም ያንቺን ታሪክ ላውቅ የቻልኩት ከእሱ ነው፡፡››
‹‹እኔ አላምንም ..ንስር ይሄን ሁሉ…. እንዴት ተደርጎ?››
‹‹አየሽ እንዳልኩሽ የእኔ ንስር ልዩ ነው..ከእኔ ጋር ያለውም ትስስር ከተፈጥሮ ክስተቶች እንደ አንድ ነው..ያም ሆኖ ግን እንዲሁ ንስር እና የሰው ልጅ ከጥንትም ጀመሮ የመንፈስ ትስስር እንደነበራቸው ታሪክ ይመሰክራል፡፡፡ሌላውን ተይና በሀገራችን ጥንታዊ ስነ ጽሁፍ ውስጥ ንስር የትንሳኤ ምልክት ነበር… በምጥቀት ማሰብ እና ወደ ከፍታ የመስፈንጠር መንፈስ ተምሳሌ ተደርጎ ይወሰድ ነበር፡፡በግብጽ ደግሞ መቃብራቸውን ጋንኤል እንዳይደፍረው የንስር ምስል ከመቃብሩ በራፍ ላይ ያስቀምጡ ነበር…ያ የንስር ምስል የጋንኤሉ መንፈስ አልፎት ወደውስጥ ሊጋባ ስለማይችል እሬሳቸው ከጥቃት የተጠበቀ ይሆናል ብለው ያምናሉ..፡፡
የጲላጦስ ሀገር የሆነችው ግሪክ ደግሞ ከአመልክቶቾ ውስጥ አንድ የሆነው የአማልዕክቶች ሁሉ ንጉስ የሆነው ዜዎስ በንስር ይመሰል እንደነበረ ይነገራል፡፡በጥንት ጊዜ አሜሪካኖች ደግሞ እጅግ ለሚያከብሩት የሌላ ወገን ሰው ያለቸውን ጥልቅ ፍቅር ሚገልጽት የንስር ላባ በመስጠት ነው፡፡በመጽሀፍ ቅዱስ ሲራክም ሶስት እራስ እና አስራ ሁለት ክንፎች ሳላለው ንስር በህልሙ ራዕይ አይቶ ነበር….የራዕይው ፍቺ በየተራ ስለሚነግሱ ነገስታት ሲገለጽለት ነበር…ንስር የኃይልን እና የስልጣን ምልክት ነው፡፡…››ስብከት የመሰለ ንግግሯዋን ተናግራ ሳትጨርስ….ዶክተሩ በራፋቸውን ከፍተው ወጡና ወደእነሱ መጡ
…‹‹.ሶፊ ደህና ነሽ?››
‹‹እንዴት አደሩ ዶክተር?››
‹‹አለሁ….ዛሬ እንግዳ ከየት አገኘሽ ?››አለት እንግዳዋ ላይ በማተኮር፡፡
‹‹አያውቋትም?››
‹‹እኔ እንጃ ከዚህ በፊት ግን ያየኋት ይመስለኛል››
‹‹አዎ ከባሌ የመጣች የአክስቴ ልጅ ነች…ከዚህ በፊትም መጥታ ስለነበረ.. ተገናኝታችኋል››
‹‹ለዛ ነዋ ፊቷ አዲስ ያልሆነብኝ….በሉ ተጫወቱ አንዲት ቀጠሮ አላለችብኝ ..ከሰዓት እንገናኛለን ..›ብለው ተሰናብተዋቸው ወደመኪናቸው ማቆሚያ ጥለዋቸው ሄዱ
ሶፊያ ሳቋ አፍኗት ስለነበር እንደራቁላት ለቀቀችው
…‹‹ሳያውቁኝ ቀርተው ነው ወይስ አውቀው ነው?››
‹‹አይ ተምታቶባቸዋል…ያው ማታ መጠጥም ስለሚወሳስዱ ነው ቅር አይበልሽ››
‹‹አረ ምን ቅር ይለኛል ነገራቸው ገርሞኝ እንጂ››ብትልም ቅር እንዳላት ግን በግልፅ ከንግግሯ ቃና በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡
‹‹እዚህ ቤት ከጥዋት ጀምሮ የሚያጋጥምሽ ነገር ሁሉ ይገርማል አይደል?››
‹‹ምን መገረም ብቻ ከአዕምሮም በላይ ነው….እኔ እንዲህ….››ንግግሯን ሳትጨርስ ንስሩ እየተምዘገዘገ መጣና ከእነሱ ፊት ለፊት በአምስት ሜትር ርቀት ያህል በሚገኝ የጽድ ዛፍ ላይ ሲያርፍ ስለተመለከተች አቆረጠችና …ምን እንደሚከሰት ለማወቅ መጎጎቷን በሚያስታውቅባት መንፈስ‹‹መጣ ››አለቻት፡፡
‹‹ትንሽ ታገሺኝ ››አለቻትና አዕምሮዋን ሰብሰባ ትኩረቷን በሙሉ ከንስሯ ጋር በማቋራኘት እምሮውን ማንበብ ጀመረች፡፡
‹‹መምጣትሽን ፍቅረኛሽ አያውቅም አይደል?፡፡››
‹‹አዎ..አንዴ በእሱ ክህደትና ዘረፋ የሞትኩት አንሶኝ ጭራሽ መምጣቴን ነግሬው ስሩ ቆሜ ሁለተኛ ሞት ልሙት እንዴ? አላደርገውም ….ፍቅሬን መልስልኝ ብዬ ልማፀነው..?ወይስ ብሬን መልስልኝ ልበለው?››
በንስሯ አእምሮ አሻግራ እያየች ያለችው ታሪክ አሰገርሟት፡፡‹‹ቆይ ቆይ…በዚህ ሰዓት ፍቅረኛሽ ምን እየሰራ እንደሆነ ታውቂያለሽ…?››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ምን እየሰራ ነው..?.ከሚስቱ እየተዳራ ወይም ልጁን እያጫወተ ይሆናል››ብስጭት እና ቅናት በተቀላቀለበት ድምፀት መለሰችላት፡፡
‹‹አይደለም …ትናንትና ወደ ጊኒጪ ሄዶ እናትሽን አምጥቶ ግሩም ጠቅላላ ሆስፒታል እያሳከማቸው ነው…››
‹‹የእኔን እናት .. ?ምን ሆና ነው…?››በድንጋጤና በመገረም .እናም ደግሞ ባለማመን ጠየቀች፡፡
‹‹አትደንግጪ ያው የተለመደው በሽታዋ ነው….ድሮም ከፍተኛ የጨጎራ ቁስለት እንዳለባት ታውቂያለሽ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››
‹‹ግን እኔን እንዲህ አድርጎኝ እንዴት ያሰጠጉታል …እናቴ ምንም የሚያስታምማት እና ሚያሳክማት ሰው ብታጣ እንዴት ልጇን ከከዳ ሰው ጋር ትተባበረለች…?እኔ ይሄን ማመን አልችልም …፡፡ሌላው ይቅር እናቴ እንኳን ለስላሳ እና የዋህ ስለሆነች ይቅር ልትለው ትችላለች… እህቴ ግን እርግጠኛ ነኝ ይቅር አትለውም ፤ እርግጥ ሁሉም ለእሱ የላኩለትን ብር አያውቁም …ግን በጣም እንደማፈቅረውና ላገባውም እንደምፈልግ ከዛም አልፎ ቃል እንደተግባባን ግን በደንብ ያውቃሉ፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ…በጣም ነው የሚያፈቅርሽ፡፡››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ከልጅቷ ጋር ሲያወሩ እና ከቤት ሲወጡ ሶስት ሰዓት ሆነ….‹‹ፍቅረኛሽ አሁን የት ነው የሚኖረው?፡፡››ጠየቀቻት፡፡
‹‹እዚሁ አዲስ አበባ ቤቴል አካባቢ እቤተሰቦቹ ያወረሱት ቤት ውስጥ ነው የሚኖረው፡፡››
‹‹ፎቶው አለሽ?››
‹‹አዎ›› ብላት ሞባይሏን ከፈተችና አሳየቻት፡፡ሞባይሏን ተቀብላ ተመለከተችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ‹‹ተከተይኝ ››አለቻት እና ወደበረንዳው ወጡ…ንስሯ ተረጋግቶ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ስታየው እንደመፍራትም ግራ እንደመጋባትም አለችና፡፡
‹‹ምን አይነት አሞራ ነው..አይፈራም እንዴ? ››
‹‹የእኔ ነው››
‹‹አሞራው?››
‹‹አዎ…ግን አሞራ ሳይሆን ንስር ነው…የእኔ ንሰር ፡፡››
‹‹ምን ያደርግልሻል?፡፡››
‹‹እሱማ ለእኔ ብዙ ነገሬ ነው… የፈለኩትን ነገር ያደርግልኛል..እኔ እንደውም የሚገርመኝ እኔ ለእሱ ምን አደርግለታለሁ ሚለውን ነው››
‹‹ይቅርታ ግን ያስፈራል…. .በተለይ አይኖቹ እና መንቁሩ…››እሷን ችላ አለቻትና ሞባይሏ ላይ ያለውን የልጅቷን ፍቅረኛ ፎቶ ለንስሯ እያሳየች ‹‹….እንርዳት መሰለኝ…እወነቱን ማወቅ መብት አላት››ስትለው ክንፎቹን አርገፈገፈና መቀመጫውን ለቆ በአየር ላይ ተንሳፈፈ…እሷ በርግጋ ወደኃላዋ አፈገፈገች….ወደላይ ተምዘግዝጎ አየሩን እየሰነጠቀ ከፍታውን ለአይን መታየት እሰከማይችል ድረስ ርቆ ተሰወረ፡
‹‹ቁጭ በይ› አለቻትና በረንዳው ላይ ካለው ወንበር አንዱን እያሳየቻት እሷ ንስሯ በለቀቀላት ወንበር ላይ እየተቀመጠች፡፡
‹‹ሄደብሽ እኮ …እንዲህ እርቆ ሄዶ አሁን አውቆ ተመልሶ ይመጣል?፡፡››
‹‹አዎ የእኔ እወቀት ዘጠና ፐርሰንቱ ከእሱ የማገኘው ነው…ንስሮች በተፈጥሮቸው በጣም ልዩ የሆኑ የአእዋፋት ዝርያዎች ናቸው፡፡እይታቸውም ጥልቅ አስተሳሰባቸውም ስል እና የተሞረደ ነው፡፡ከዛም በላይ ግን የእኔ ንስር የተለየ ነው፡፡እንዴት የሚለውን ነገር ላብራራልሽ አልችልም..ግን አሁን የሚያደርገውን ታያለሽ ..ከዛ እራስሽ ትፈርጂያለሽ››
‹‹እንዴት?››
‹‹አሁን ፍቅረኛሽን ፎቶ እያሳየሁት ሳወራው አላየሽም?››
‹‹አይቻለው.ግን እናቴም ሲጨንቃት እና በሆዷ ነገር ሲገባ ከምታልባት ላም ጋር ታወራ ነበር…እንደውም ለእሱ ስታወሪ እናቴ ነች ትዝ ያለችኝ፡፡››
‹‹አይ ይሄ ይለያል..አሁን ያንችን ችግር ማለት ስለፍቅረኛሽ ትክክለኛ ነገር እንዲያጣራልኝ ነው የላኩት››
‹‹እንዲት አድርጎ››
‹‹በቃ የተለየ ችሎታ አለው… ማንኛውም ነገር ካተኮረበት የውስጡን ሀሳብ እና ጠቅላላ ታሪኩን ማንበብ ይችላል…እኔ ደግሞ ከሱ አዕምሮ ማንበብ እችላለሁ..ወይም እንዳውቀው አዕምሮውን ይከፍትልኛል..ቅድም ያንቺን ታሪክ ላውቅ የቻልኩት ከእሱ ነው፡፡››
‹‹እኔ አላምንም ..ንስር ይሄን ሁሉ…. እንዴት ተደርጎ?››
‹‹አየሽ እንዳልኩሽ የእኔ ንስር ልዩ ነው..ከእኔ ጋር ያለውም ትስስር ከተፈጥሮ ክስተቶች እንደ አንድ ነው..ያም ሆኖ ግን እንዲሁ ንስር እና የሰው ልጅ ከጥንትም ጀመሮ የመንፈስ ትስስር እንደነበራቸው ታሪክ ይመሰክራል፡፡፡ሌላውን ተይና በሀገራችን ጥንታዊ ስነ ጽሁፍ ውስጥ ንስር የትንሳኤ ምልክት ነበር… በምጥቀት ማሰብ እና ወደ ከፍታ የመስፈንጠር መንፈስ ተምሳሌ ተደርጎ ይወሰድ ነበር፡፡በግብጽ ደግሞ መቃብራቸውን ጋንኤል እንዳይደፍረው የንስር ምስል ከመቃብሩ በራፍ ላይ ያስቀምጡ ነበር…ያ የንስር ምስል የጋንኤሉ መንፈስ አልፎት ወደውስጥ ሊጋባ ስለማይችል እሬሳቸው ከጥቃት የተጠበቀ ይሆናል ብለው ያምናሉ..፡፡
የጲላጦስ ሀገር የሆነችው ግሪክ ደግሞ ከአመልክቶቾ ውስጥ አንድ የሆነው የአማልዕክቶች ሁሉ ንጉስ የሆነው ዜዎስ በንስር ይመሰል እንደነበረ ይነገራል፡፡በጥንት ጊዜ አሜሪካኖች ደግሞ እጅግ ለሚያከብሩት የሌላ ወገን ሰው ያለቸውን ጥልቅ ፍቅር ሚገልጽት የንስር ላባ በመስጠት ነው፡፡በመጽሀፍ ቅዱስ ሲራክም ሶስት እራስ እና አስራ ሁለት ክንፎች ሳላለው ንስር በህልሙ ራዕይ አይቶ ነበር….የራዕይው ፍቺ በየተራ ስለሚነግሱ ነገስታት ሲገለጽለት ነበር…ንስር የኃይልን እና የስልጣን ምልክት ነው፡፡…››ስብከት የመሰለ ንግግሯዋን ተናግራ ሳትጨርስ….ዶክተሩ በራፋቸውን ከፍተው ወጡና ወደእነሱ መጡ
…‹‹.ሶፊ ደህና ነሽ?››
‹‹እንዴት አደሩ ዶክተር?››
‹‹አለሁ….ዛሬ እንግዳ ከየት አገኘሽ ?››አለት እንግዳዋ ላይ በማተኮር፡፡
‹‹አያውቋትም?››
‹‹እኔ እንጃ ከዚህ በፊት ግን ያየኋት ይመስለኛል››
‹‹አዎ ከባሌ የመጣች የአክስቴ ልጅ ነች…ከዚህ በፊትም መጥታ ስለነበረ.. ተገናኝታችኋል››
‹‹ለዛ ነዋ ፊቷ አዲስ ያልሆነብኝ….በሉ ተጫወቱ አንዲት ቀጠሮ አላለችብኝ ..ከሰዓት እንገናኛለን ..›ብለው ተሰናብተዋቸው ወደመኪናቸው ማቆሚያ ጥለዋቸው ሄዱ
ሶፊያ ሳቋ አፍኗት ስለነበር እንደራቁላት ለቀቀችው
…‹‹ሳያውቁኝ ቀርተው ነው ወይስ አውቀው ነው?››
‹‹አይ ተምታቶባቸዋል…ያው ማታ መጠጥም ስለሚወሳስዱ ነው ቅር አይበልሽ››
‹‹አረ ምን ቅር ይለኛል ነገራቸው ገርሞኝ እንጂ››ብትልም ቅር እንዳላት ግን በግልፅ ከንግግሯ ቃና በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡
‹‹እዚህ ቤት ከጥዋት ጀምሮ የሚያጋጥምሽ ነገር ሁሉ ይገርማል አይደል?››
‹‹ምን መገረም ብቻ ከአዕምሮም በላይ ነው….እኔ እንዲህ….››ንግግሯን ሳትጨርስ ንስሩ እየተምዘገዘገ መጣና ከእነሱ ፊት ለፊት በአምስት ሜትር ርቀት ያህል በሚገኝ የጽድ ዛፍ ላይ ሲያርፍ ስለተመለከተች አቆረጠችና …ምን እንደሚከሰት ለማወቅ መጎጎቷን በሚያስታውቅባት መንፈስ‹‹መጣ ››አለቻት፡፡
‹‹ትንሽ ታገሺኝ ››አለቻትና አዕምሮዋን ሰብሰባ ትኩረቷን በሙሉ ከንስሯ ጋር በማቋራኘት እምሮውን ማንበብ ጀመረች፡፡
‹‹መምጣትሽን ፍቅረኛሽ አያውቅም አይደል?፡፡››
‹‹አዎ..አንዴ በእሱ ክህደትና ዘረፋ የሞትኩት አንሶኝ ጭራሽ መምጣቴን ነግሬው ስሩ ቆሜ ሁለተኛ ሞት ልሙት እንዴ? አላደርገውም ….ፍቅሬን መልስልኝ ብዬ ልማፀነው..?ወይስ ብሬን መልስልኝ ልበለው?››
በንስሯ አእምሮ አሻግራ እያየች ያለችው ታሪክ አሰገርሟት፡፡‹‹ቆይ ቆይ…በዚህ ሰዓት ፍቅረኛሽ ምን እየሰራ እንደሆነ ታውቂያለሽ…?››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ምን እየሰራ ነው..?.ከሚስቱ እየተዳራ ወይም ልጁን እያጫወተ ይሆናል››ብስጭት እና ቅናት በተቀላቀለበት ድምፀት መለሰችላት፡፡
‹‹አይደለም …ትናንትና ወደ ጊኒጪ ሄዶ እናትሽን አምጥቶ ግሩም ጠቅላላ ሆስፒታል እያሳከማቸው ነው…››
‹‹የእኔን እናት .. ?ምን ሆና ነው…?››በድንጋጤና በመገረም .እናም ደግሞ ባለማመን ጠየቀች፡፡
‹‹አትደንግጪ ያው የተለመደው በሽታዋ ነው….ድሮም ከፍተኛ የጨጎራ ቁስለት እንዳለባት ታውቂያለሽ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››
‹‹ግን እኔን እንዲህ አድርጎኝ እንዴት ያሰጠጉታል …እናቴ ምንም የሚያስታምማት እና ሚያሳክማት ሰው ብታጣ እንዴት ልጇን ከከዳ ሰው ጋር ትተባበረለች…?እኔ ይሄን ማመን አልችልም …፡፡ሌላው ይቅር እናቴ እንኳን ለስላሳ እና የዋህ ስለሆነች ይቅር ልትለው ትችላለች… እህቴ ግን እርግጠኛ ነኝ ይቅር አትለውም ፤ እርግጥ ሁሉም ለእሱ የላኩለትን ብር አያውቁም …ግን በጣም እንደማፈቅረውና ላገባውም እንደምፈልግ ከዛም አልፎ ቃል እንደተግባባን ግን በደንብ ያውቃሉ፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ…በጣም ነው የሚያፈቅርሽ፡፡››
👍98❤6👎2🥰2👏2🔥1😢1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
""
‹‹ምን መሰለሽ ፍቅር በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ከብረሀናማ ቀለማቶች የተሸመነ ጥልቁ ስሜት ነው፡፡ፍቅር ወደ ወደድነው ሰው ልብ ውስጥ ሰተት ብለን የምንገባበትን በር የምንከፍትበት ማስተር ኪይ ነው፡፡ፍቅር ስለእራሳችን በተለየ መልኩ እንድናስብ የሚያስገድደን የተቀደሰ የዕይታ ብሌናችን ነው፡፡በፍቅር የተነደፈ ደሀ በውስጡ የሚሰማው አለም ሁሉ የእሱ ንብረት እንደሆነችና አውቆና ንቆ እንደተዋት ነው …የተናቀ እና መጠጊያ አልባው ሰው በፍቅር እቅፍ ውስጥ ሲወድቅ የንግስና ዙፋኑ የእሱ እንደሆነ እና አለም ጠቅላላ ወደእሱ አጎንብሳ እየሰገደችለት እንደሆነ ነው የሚሰማው፡፡
የስልጣን ማማ ላይ ተቆናጦ ልቡ በትዕቢት ያበጠ በፍቅር አዳልጦት ሲዘረጥጥ ..እንዴ ለካ እኔም ሰው ነኝ…?ለካ ማንበርከክ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለመንበርከክም እገደዳለሁ? ብሎ እንዲያስብ ያደርገዋል፡፡ ….ሰውን ሞት እና መቃብር ብቻ ሳይሆን ፍቅርም ወደ አንድ ተመሳሳይ ስሜት በመጎተት ያቀራርበዋል፡፡…..ግን አሳዛኙ ነገር ይሄ ቅዱሱ ፍቅር ብዙ ጊዜ ድምጥማጡ የሚጠፋው በማይረባ ትርኪ ሚርኪ እውነትነታቸው ባልተረጋገጡ ጉዳዬች ነው…..ባለመደማመጥ እና ባልተጣራ ወሬ የተነሳ ነው፡፡
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹ፍቅረኛሽ እንዳገባ ማን ነው የነገረሽ……..? ››
‹‹ከእስር ቤት ወጥቼ ተጠርዥ ልመጣ ስል አንድ እዛ የምትኖር ጓደኛዬ ከአሰሪዎቼ ቤት የነበረኝን ሻንጣዬን አውጥታ እሷ ጋር አድርጋልኝ ስለነበር…ስትሸኝ አቀብላኝ ነበር ፡፡ይቺ ጓደኛዬ ..በጣም ጥሩ ሰው ነች ለኪስ የሚሆነኝን ትንሽ ብር የሰጠችኝም እሷ ነበረች.. ወደ ኢትዬጵያ የገባሁትም በለሊት ስለነበረ ሆቴል ነበር የያዝኩት እና በሰላም መግባቴን ለመናገር ለጓደኛዬ ስልክ ደወልኩላት፡፡ ፖስታ ከኢትዬጵያ መቶልኝ እንደነበረ እና ሻንጣ ኪስ ውስጥ ከታልኝ ሳትነገርኝ እንደረሳችው ነገረችኝ፤ስፈልገው አገኘሁት፡፡
‹‹ስልክ ባልደውልላት እና እሷም አስታውሳ ባትነግረኝ ኖሮ አላየውም ነበር…ቀጥታ ፍቅረኛዬ ቤት ሄጄ ስርፕራይዝ ላደርገው ነበር እቅዴ..እሱ ጋር አንድ ሶስት ቀን አሳልፌ እና አገግሜ ወደጊንጪ ቤተሰቦቼ ጋር ልሄድ ነበር ያሰብኩት..››
ፖስታውን ስከፍተው ግን በቃ የሲኦልን በር እንደመክፍት ቁጠሪው፣…ውስጡ ሲኦላዊ የክህደት እሳት ነበር ያለው..አገባዋለሁ ብዬ ሳልመው የነበረው ሰውዬ የአንድ አመት ህጻን አቅፎ ሲያባብል የተነሳው ፎቶ ነው፡፡ከመከራዬ አገግምበታላሁ ከስባራቴ እጠገንበታላሁ ያልኩት ሰው ጭራሽ መከራዬን የሚጨምር.ስብራቴን የሚያባብስ ሆኖ ጠበቀኝ…..ከፎቶ ጀርባ ላይ….. ናሆም ፍቃዱ እንኳንም ለአንደኛ አመት ልደት አደረሰህ ይላል፡፡ምድር ተሰንጥቃ ብትውጠኝ እወድ ነበር….ምን አይነት ክህደት ነው…?አላስቻለኝም እወነቱን ለማወቅ ጭለማን ተገን አድርጌ ሰፈሩ ሄድኩ….አድፍጬ በአጥር ቀዳዳ አጨንቁሬ ግቢውን ለሰዓታት ቃኘሁ…እውነት ነበረ ፤ልጅ አቅፎ ግቢ ውስጥ እየተዘዋወረ ሲያባብል እና ሲያጫውት አየሁት…በወለብታ ነው እንጂ ሚስቱንም በመጠኑ አይቼያታለሁ››
‹‹ማንነቷን ግን አላየሽም? ››
‹‹ማንነቷ ምን ይሰራልኛል…ሮማንንም አገባ ቦንቱን ለእኔ ምንስ ሲጨምርልኝ ምንስ ሲቀንስልኝ?››
‹‹አይ ማንነቷን እስክታውቂ በደንብ ብታጣሪ..ወይንም እሱን በአካል አግኝተሸ ለምን እንደዛ አደረግክ? ብለሽ ብትጠይቂው ጥሩ ነበረ ….ሁለት ሳምንት ሙሉ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆነሽ አትሰቃይም ነበር..በማትፈልጊውን የህይወት መስመር አትጀምሪም ነበር.ብዙ ጊዜ አውነትን ለማደን ብለን እንደ ጀግና መንግድ እንጀምርና ገና የጫካው መግቢያ ጋር ስንደርስ ብርክ ይዞን እንመለሳለን፤ ቀስታችንን እዛው ጨርሰን ወደኃላ እንመለሳለን.ኩልል እና ጥርት ያለውን እውነት ለማግኘት ግን የጫካው እንብርት ድረስ በእሾኩ እየተወጉ እና በፍርሀት እየራዱ መጓዝን ይጠይቃል ››
‹‹አልገባኝም››አለቻት ኮስተር ብላ
‹‹ንብረትሽ..ማለት አንቺ ለፍቅረኛሽ የላክሽው ብር በእጥፍ ጨምሮ አንቺኑ እየጠበቀሽ ነው››
‹‹እንዴት?››
‹‹በላክሽው 300 ሺ ብር ላይ የራሱን ብር ጨምሮ ሚኒባስ ገዝቶበታል››
‹‹እኮ እሱንማ ግቢው ውስጥ ቆማ አይቼያለሁ፡ግን አሁን ንብረትሽ ነው ብሎ የሚመልስልኝ ይመስልሻል…?ልመልስልሽስ ቢል ሚስቱ እሺ ትለዋለች..?እኔስ አሱ ፊት ቆሜ ብሬን ስጠኝ አትስጠየኝ ብዬ የመከራከሩ ጉልበት ይኖረኛል?፡፡›
‹‹ሚኒባሶ በቀን የምትሰራው ብር ያንቺ ድርሻ በስምሽ በተከፈተ የባንክ ደብተር እያስቀመጠልሽ ነው…በጥሬ ብር ደረጃ መቶ ሳላሳ ሺብር ባንክ ተቀምጦልሻል…..ሚኒባሶም ባንቺ ስም ነች፡፡››
‹‹እንዴት ተደርጎ?››
‹‹በቃ በጣም የሚያፈቅርሽ እና ላንቺም ብቻ ሳይሆን ለቤተሰቦችሽም የሚኖር እና የሚጨነቅ መልካም ልጅ ነው››
‹‹አይ ያደረገው ነገር እወነት እንዳልሺው ከሆነ ዘራፊ አያሰኘው ይሆናል.. ነገር ግን ፍቅሬን ትቶ ሌላ አግብቶ ሌላ ልጅ መውለዱ ግን ከከዳተኛነት ውጭ ሌላ ስያሜ ሊሰጠው አይችልም ፡፡
‹‹አሁን ቀጥ ብለሽ ዛሬውኑ እቤቱ ሂጂ››
‹‹ምን ልፈጥር?››
‹‹ሂጂ አልኩሽ ሂጂ.››
‹‹ሄጄስ?››
‹‹በቃ ግቢውን አንኳኩተሸ ግቢ..ከዛ የሚሆነው ነገር ይሆናል…ይሄንን ካላደረግሽ ግን ህይወትሽን ሙሉ ምትፀፀችበትን ስህተት ነው የምትሰሪው››በብዙ ምክር እና ከማስፈራሪያ በኃላ አሳምናት ሸኘቻት….
….ከዚህ በላይ ልትነግራት አልፈለገችም..እራሷ በሂደቱ ውስጥ እንድታጣጥመው ነው የፈለገችው..ፍቅረኛዋ አሁንም አልወለደም ፤አላገባምም…እሱ በምንም አይነት እሷን አልከዳትም…ለአንድ ቀን እንኳን ወስልቶባት አያውቅም..እንደውም ከዳተኛ መባል ካለበት እራሷ ነች….፡፡
እርግጥ እንዳለችው እቤቱ ውስጥ ሴት አለች…አዎ እቤት ውስጥ ልጅም አለ..የሚወደድ ናሆም የሚባል የአንድ አመት ልጅ…ሴትዬዋ ግን የገዛ እህቷ ነች….ታናሽ እህቷ ..ልጅም የእህቷ ልጅ፡፡ጊንጪ እቤተሰቦቾ ቤት ተቀምጣ የአስራሁለተኛ ክፍል ትምህርቷን በመማር ላይ እያለች አረገዘች….እሱ ሚስጥሩን ሰማ ፤ልጅቷም ህይወቷን እንዳታበላሽ ቤተሰቦቾም በኖሩበት ሀገር እንዳይሸማቀቁ ሁሉንም አሳመናቸውና ዞር አድርጎ አዲስአበባ ወደራሱ ቤት ወሰዳት….ለፍቅሩ ሲል…የእሷ ቤተሰቦች እንዳይሳቀቁ በማሰብ….. ..እሱ ጋር ተሸሽጋ ወለደች..አሁን ትምህርቷንም እየተማረች ነው፡፡››
ታዲያ ፎቶውን ማነው የላከላት..?ማን ነው እንደዛ እንድታስብ የፈለገው›…?መልሱ የገዛ እህቷ ነች፡፡በእዛች ጭንቅ ጊዜዋ ያፈቀረችውና ያረገዘችለት ሰው አፍንጫሽን ላሺ ባላት ወቅት የእህቷ ፍቅረኛ ግን እንደዛ አይዞሽ ማለቱ፤ ሽሽጎ ተንከባክቦ ጭለማውን ጊዜ እንድታልፍ ማድረጉን ..እሷን መንከባከቡ ልጇን መውደዱ ሌላ ነገር እንድታስብ አደረጋት.. የሰው ሀገር በስደት ላይ ባለችው ታላቅ እህቷ እንድትቀና ..እንድታፈቅረው…የራሴ በሆነ ብላ እንድትመኝ …
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
""
‹‹ምን መሰለሽ ፍቅር በሰው ልጅ ህይወት ውስጥ ከብረሀናማ ቀለማቶች የተሸመነ ጥልቁ ስሜት ነው፡፡ፍቅር ወደ ወደድነው ሰው ልብ ውስጥ ሰተት ብለን የምንገባበትን በር የምንከፍትበት ማስተር ኪይ ነው፡፡ፍቅር ስለእራሳችን በተለየ መልኩ እንድናስብ የሚያስገድደን የተቀደሰ የዕይታ ብሌናችን ነው፡፡በፍቅር የተነደፈ ደሀ በውስጡ የሚሰማው አለም ሁሉ የእሱ ንብረት እንደሆነችና አውቆና ንቆ እንደተዋት ነው …የተናቀ እና መጠጊያ አልባው ሰው በፍቅር እቅፍ ውስጥ ሲወድቅ የንግስና ዙፋኑ የእሱ እንደሆነ እና አለም ጠቅላላ ወደእሱ አጎንብሳ እየሰገደችለት እንደሆነ ነው የሚሰማው፡፡
የስልጣን ማማ ላይ ተቆናጦ ልቡ በትዕቢት ያበጠ በፍቅር አዳልጦት ሲዘረጥጥ ..እንዴ ለካ እኔም ሰው ነኝ…?ለካ ማንበርከክ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለመንበርከክም እገደዳለሁ? ብሎ እንዲያስብ ያደርገዋል፡፡ ….ሰውን ሞት እና መቃብር ብቻ ሳይሆን ፍቅርም ወደ አንድ ተመሳሳይ ስሜት በመጎተት ያቀራርበዋል፡፡…..ግን አሳዛኙ ነገር ይሄ ቅዱሱ ፍቅር ብዙ ጊዜ ድምጥማጡ የሚጠፋው በማይረባ ትርኪ ሚርኪ እውነትነታቸው ባልተረጋገጡ ጉዳዬች ነው…..ባለመደማመጥ እና ባልተጣራ ወሬ የተነሳ ነው፡፡
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹ፍቅረኛሽ እንዳገባ ማን ነው የነገረሽ……..? ››
‹‹ከእስር ቤት ወጥቼ ተጠርዥ ልመጣ ስል አንድ እዛ የምትኖር ጓደኛዬ ከአሰሪዎቼ ቤት የነበረኝን ሻንጣዬን አውጥታ እሷ ጋር አድርጋልኝ ስለነበር…ስትሸኝ አቀብላኝ ነበር ፡፡ይቺ ጓደኛዬ ..በጣም ጥሩ ሰው ነች ለኪስ የሚሆነኝን ትንሽ ብር የሰጠችኝም እሷ ነበረች.. ወደ ኢትዬጵያ የገባሁትም በለሊት ስለነበረ ሆቴል ነበር የያዝኩት እና በሰላም መግባቴን ለመናገር ለጓደኛዬ ስልክ ደወልኩላት፡፡ ፖስታ ከኢትዬጵያ መቶልኝ እንደነበረ እና ሻንጣ ኪስ ውስጥ ከታልኝ ሳትነገርኝ እንደረሳችው ነገረችኝ፤ስፈልገው አገኘሁት፡፡
‹‹ስልክ ባልደውልላት እና እሷም አስታውሳ ባትነግረኝ ኖሮ አላየውም ነበር…ቀጥታ ፍቅረኛዬ ቤት ሄጄ ስርፕራይዝ ላደርገው ነበር እቅዴ..እሱ ጋር አንድ ሶስት ቀን አሳልፌ እና አገግሜ ወደጊንጪ ቤተሰቦቼ ጋር ልሄድ ነበር ያሰብኩት..››
ፖስታውን ስከፍተው ግን በቃ የሲኦልን በር እንደመክፍት ቁጠሪው፣…ውስጡ ሲኦላዊ የክህደት እሳት ነበር ያለው..አገባዋለሁ ብዬ ሳልመው የነበረው ሰውዬ የአንድ አመት ህጻን አቅፎ ሲያባብል የተነሳው ፎቶ ነው፡፡ከመከራዬ አገግምበታላሁ ከስባራቴ እጠገንበታላሁ ያልኩት ሰው ጭራሽ መከራዬን የሚጨምር.ስብራቴን የሚያባብስ ሆኖ ጠበቀኝ…..ከፎቶ ጀርባ ላይ….. ናሆም ፍቃዱ እንኳንም ለአንደኛ አመት ልደት አደረሰህ ይላል፡፡ምድር ተሰንጥቃ ብትውጠኝ እወድ ነበር….ምን አይነት ክህደት ነው…?አላስቻለኝም እወነቱን ለማወቅ ጭለማን ተገን አድርጌ ሰፈሩ ሄድኩ….አድፍጬ በአጥር ቀዳዳ አጨንቁሬ ግቢውን ለሰዓታት ቃኘሁ…እውነት ነበረ ፤ልጅ አቅፎ ግቢ ውስጥ እየተዘዋወረ ሲያባብል እና ሲያጫውት አየሁት…በወለብታ ነው እንጂ ሚስቱንም በመጠኑ አይቼያታለሁ››
‹‹ማንነቷን ግን አላየሽም? ››
‹‹ማንነቷ ምን ይሰራልኛል…ሮማንንም አገባ ቦንቱን ለእኔ ምንስ ሲጨምርልኝ ምንስ ሲቀንስልኝ?››
‹‹አይ ማንነቷን እስክታውቂ በደንብ ብታጣሪ..ወይንም እሱን በአካል አግኝተሸ ለምን እንደዛ አደረግክ? ብለሽ ብትጠይቂው ጥሩ ነበረ ….ሁለት ሳምንት ሙሉ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆነሽ አትሰቃይም ነበር..በማትፈልጊውን የህይወት መስመር አትጀምሪም ነበር.ብዙ ጊዜ አውነትን ለማደን ብለን እንደ ጀግና መንግድ እንጀምርና ገና የጫካው መግቢያ ጋር ስንደርስ ብርክ ይዞን እንመለሳለን፤ ቀስታችንን እዛው ጨርሰን ወደኃላ እንመለሳለን.ኩልል እና ጥርት ያለውን እውነት ለማግኘት ግን የጫካው እንብርት ድረስ በእሾኩ እየተወጉ እና በፍርሀት እየራዱ መጓዝን ይጠይቃል ››
‹‹አልገባኝም››አለቻት ኮስተር ብላ
‹‹ንብረትሽ..ማለት አንቺ ለፍቅረኛሽ የላክሽው ብር በእጥፍ ጨምሮ አንቺኑ እየጠበቀሽ ነው››
‹‹እንዴት?››
‹‹በላክሽው 300 ሺ ብር ላይ የራሱን ብር ጨምሮ ሚኒባስ ገዝቶበታል››
‹‹እኮ እሱንማ ግቢው ውስጥ ቆማ አይቼያለሁ፡ግን አሁን ንብረትሽ ነው ብሎ የሚመልስልኝ ይመስልሻል…?ልመልስልሽስ ቢል ሚስቱ እሺ ትለዋለች..?እኔስ አሱ ፊት ቆሜ ብሬን ስጠኝ አትስጠየኝ ብዬ የመከራከሩ ጉልበት ይኖረኛል?፡፡›
‹‹ሚኒባሶ በቀን የምትሰራው ብር ያንቺ ድርሻ በስምሽ በተከፈተ የባንክ ደብተር እያስቀመጠልሽ ነው…በጥሬ ብር ደረጃ መቶ ሳላሳ ሺብር ባንክ ተቀምጦልሻል…..ሚኒባሶም ባንቺ ስም ነች፡፡››
‹‹እንዴት ተደርጎ?››
‹‹በቃ በጣም የሚያፈቅርሽ እና ላንቺም ብቻ ሳይሆን ለቤተሰቦችሽም የሚኖር እና የሚጨነቅ መልካም ልጅ ነው››
‹‹አይ ያደረገው ነገር እወነት እንዳልሺው ከሆነ ዘራፊ አያሰኘው ይሆናል.. ነገር ግን ፍቅሬን ትቶ ሌላ አግብቶ ሌላ ልጅ መውለዱ ግን ከከዳተኛነት ውጭ ሌላ ስያሜ ሊሰጠው አይችልም ፡፡
‹‹አሁን ቀጥ ብለሽ ዛሬውኑ እቤቱ ሂጂ››
‹‹ምን ልፈጥር?››
‹‹ሂጂ አልኩሽ ሂጂ.››
‹‹ሄጄስ?››
‹‹በቃ ግቢውን አንኳኩተሸ ግቢ..ከዛ የሚሆነው ነገር ይሆናል…ይሄንን ካላደረግሽ ግን ህይወትሽን ሙሉ ምትፀፀችበትን ስህተት ነው የምትሰሪው››በብዙ ምክር እና ከማስፈራሪያ በኃላ አሳምናት ሸኘቻት….
….ከዚህ በላይ ልትነግራት አልፈለገችም..እራሷ በሂደቱ ውስጥ እንድታጣጥመው ነው የፈለገችው..ፍቅረኛዋ አሁንም አልወለደም ፤አላገባምም…እሱ በምንም አይነት እሷን አልከዳትም…ለአንድ ቀን እንኳን ወስልቶባት አያውቅም..እንደውም ከዳተኛ መባል ካለበት እራሷ ነች….፡፡
እርግጥ እንዳለችው እቤቱ ውስጥ ሴት አለች…አዎ እቤት ውስጥ ልጅም አለ..የሚወደድ ናሆም የሚባል የአንድ አመት ልጅ…ሴትዬዋ ግን የገዛ እህቷ ነች….ታናሽ እህቷ ..ልጅም የእህቷ ልጅ፡፡ጊንጪ እቤተሰቦቾ ቤት ተቀምጣ የአስራሁለተኛ ክፍል ትምህርቷን በመማር ላይ እያለች አረገዘች….እሱ ሚስጥሩን ሰማ ፤ልጅቷም ህይወቷን እንዳታበላሽ ቤተሰቦቾም በኖሩበት ሀገር እንዳይሸማቀቁ ሁሉንም አሳመናቸውና ዞር አድርጎ አዲስአበባ ወደራሱ ቤት ወሰዳት….ለፍቅሩ ሲል…የእሷ ቤተሰቦች እንዳይሳቀቁ በማሰብ….. ..እሱ ጋር ተሸሽጋ ወለደች..አሁን ትምህርቷንም እየተማረች ነው፡፡››
ታዲያ ፎቶውን ማነው የላከላት..?ማን ነው እንደዛ እንድታስብ የፈለገው›…?መልሱ የገዛ እህቷ ነች፡፡በእዛች ጭንቅ ጊዜዋ ያፈቀረችውና ያረገዘችለት ሰው አፍንጫሽን ላሺ ባላት ወቅት የእህቷ ፍቅረኛ ግን እንደዛ አይዞሽ ማለቱ፤ ሽሽጎ ተንከባክቦ ጭለማውን ጊዜ እንድታልፍ ማድረጉን ..እሷን መንከባከቡ ልጇን መውደዱ ሌላ ነገር እንድታስብ አደረጋት.. የሰው ሀገር በስደት ላይ ባለችው ታላቅ እህቷ እንድትቀና ..እንድታፈቅረው…የራሴ በሆነ ብላ እንድትመኝ …
👍96❤12👏2👎1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
ኬድሮን ከምሽቱ 11 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ደባበራት እና ከቤቷ ወጣች… ቦሌ አካባቢ ወደሚገኝ ሰሞኑን ወደተከፈተ አንድ ሆቴል ነው እየሄደች ያለችው ..መኪናዋን ሆቴሉ ግቢ ውስጥ በማስገባት ምቹ ቦታ ፈልጋ አቆመችና የለበስችውን ልብስ እዛው ከመኪናዋ ሳትወርድ አወላልቃ የዋና ልብሷን በመልበስ ወደ ዋና ጋንዳው አመራች ..ሰውነቷን ጭፍግግ ስላለት ዘና ማለት ነው የፈለገችው….በዋና ሰውነቷን ማፍታታት……
የዋና ገንዳው አካባቢ እንደደረሰች ዘላ ውሀ ውስጥ ገብታ መንቦጫረቅ አልፈለገችም…የመዋኛ ገንዳውን ዙሪያ ከበው ወደ ተዘረጉ ዘመናዊ ወንበሮች ሄደችና ..ባዳውን ከሆነ አንድ ወንበር ላይ ዘና ብላ በመቀመጥ የሚዋኙትን ታዳሚዎች እያየችና እየታዘበች መዝናናቷን ቀጠለች…..
…..አበሻም ፈረንጆችም…. ሴቶችም ወንዶችም… ህፃናትም፤ ወጣትና አሮጊቶችም በስብጥር ሲዋኙ እና ሲንቦጫረቁ ይታያሉ….
ስሜቷ አንቀልቅሎ ወደ እዚህ ስፍራ ያመጣት ለምን እንደሆነ እስከአሁን አልተገለፀላትም .. …?….. ድንገት ግን ሳታስብ አንድ ወጣት ዕድሜው በግምት በ25 30 ዓመት መካከል የሚገኝ ወንድ ላይ አይኗ አረፈ…ያምራል… በጣም ነው የሚያምረው..፡፡ ከደረቱ በላይ ያለው የሰውነት ቅርጽ ውጥርጥር ያለ እና ሚማርክ ነው…ፀጉሩ በውሀው አቅም ተሸንፎ በሚመስል ሁኔታ ዝልፍልፍ ብሎ ግንባሩ ላይ ተዘናፍሏል፡፡አይኖቹ ከጨረቃ የተዋሳቸው ይመስላሉ…ኪሊማንጀሮ ተራራ ጫፍ ላይ ያገኘችውን አንድሪውን አስታወሳት፡፡.
እሷ ደግሞ ካለ ችግሯ ወይም ድክመት ሊባልም ይችላል ስድስት ወር ወይም አመት ምንም ወንድ ሳያምራት ወይም ከምንም አይነት ወንድ ጋር ሳትነካካ ትቆይና ድንገት በሰከንድ ውስጥ በእይታዋ ውስጥ የሆነ ወንድ ገብቶ ቀልቧን ከሰረቀት በቃ..ስግብግብ ነው የምትለው..፡፡በዛኑ ቀን ወይም ከተቻለም በዛኑ ደቂቃ ማግኘትና አምሮቷን መወጣት አለባት….(ያው የእሷ ፍቅር ከአንድ ጊዜ የወሲብ ፍላጎት አያልፍም ..ከዛ በላይ ፈልጋ አታውቅም ..ለእሷ በፍቅር መነሁለል እና . ወንድን እየተከተሉ መዞር ወይም ወንድ አፈቀርኩሽ እያለ ለሀጩን እያዝረበረበ በዙሪያዋ እንዲሽከረከርባት በፍፅም አትፈቅድም….)
.የእሷ ችግር ጊዜያዊ ነው ..ጊዜያዊም ብቻ ሳይሆን ቅፅበታዊም ጭምር ነው….በፈለገች ጊዜ ማግኘት አለባት… .ካለበለዛ እራሷን ሁሉ መቆጣጠር ስለሚያቅታት ጥፋት ታጠፋለች....የማይሰራ ስራ ትሰራለች…የወሲብ ጠኔም በቀላሉ አዙሮ እና አጥወልውሎ ሊደፋት ሁሉ ይችላል….እና አሁንም ይሄ ሻንቂላ ወንዳ ወንድ ወጣት እፊቷ ያለው ሰማያዊ መዋኛ ገንዳ ውስጥ ጥበባዊ በሆነ ስልት እንደ ዓሳ ነባሪ ብቅ ጥልቅ በማለት እየዋኘ ቀልቧን ስልብልብ አድርጎታል..
‹‹ተይ ይቅርብሽ››እራሷን ለመገሰፅ ሞከረች…እራሷን መገደብ እንደማይሳካላት ግን ከልምድ ታውቃለች… …..ከለበሰችው የዋና ልብስ ስር እግሯ እና እግሯ መካከል ያሳክከት ጀመረ.. እጣቷን ወደ ጭኗ መካከል በመስደድ የሚበላትን አካባቢ አከክ…አከ…ክ አድርጋ ተንፈስ ለማለት አሰበችና ዙሪያዋን በሰዎች መከበቧን ሳታስተውል መልሳ ተወችው....ከተቀመጠችበት መቀመጫ ተነሳችና ወደዋናው ገንዳ ቀረበች…ምን ማድረግ እንዳለባት እያሰበች ነው…ድንገት በትይዩ አቅጣጫ በሰማዩ ላይ በሶስት መቶ ሜትር ርቀት …. ንስራ ሲያንጃብብ ተመለከተችና
‹‹…ወይ ከመቼው ተከትሎኝ መጣ….ግን እንኳን መጣህ.››ስትል በውስጧ አጉረመረመች…. እሱን በአቅራቢያዋ በማየቷ ደስ አላት..አዎ ይሄ ቀልቧ ያረፈበትን ወጣት ከተቻለ አሁን ለመክሰስ..ካልሆነም ለእራት ለማድረስ የእሱ እርዳታ ያስፈልጋታል….ስለደካማ ጎኑ በእነዛ ሰርሳሪ አይኖቹ በማየት ካልነገረራትና በምን ሁኔታ ብትቀርበው የሀሳቧ ሊሳካ እንደሚችል መረጃውን ካላቀበላት ባሰበችው ፍጥነት ሊሰካላት አይችልም ፡፡
ደስታዋ ግን ሀሳቡን አስባ ሳትጨርስ ነው ከውስጧ በኖ የጠፋው….የንስሯን እርዳታ መጠቀም አትችልም…ምክንያቱም ይሄ ሰው ምን አልባት የማይሆን ታሪክ ካለው..ወይም አደጋኛ ሰው ከሆነ ንስሯ የሆነ ተአምር ፈጥሮ ከእሱ ጋር በምንም አይነት ተአምር እንዳትገናኝ ያደርጋታል..በምኞቷ መካከል ጣልቃ ይገባና ያጨናግፍባታል…ያ እንዲሆን ደግሞ አትፈልግም...ስለዚህ እዚህ ታሪክ ውስጥ ንስሯን አታሳትፈውም፡፡እንደዛ ወሰነች፡፡
..እንዳዛ ከሆነ ደግሞ እየበላት ያለውን በገዛ ጣቶቾ ስታክ ማደራ ነው…ፈርዶባት ደግሞ በአንዱ የተቀሰቀውን ስሜቷ በሌላ ወንድ አካክሳ ልታበርደው አትችልም…ይሄ የእሷ የሆነ ልዩ ባህሪ ነው……
ስለዚህ ይሄን ጉዳይ በራሷ መወጣት አለባት….."ንስሯን ምንም እርዳታ አልጠይቀውም….እሱ በሚዋኝበት አካባቢ እስትራቴጂካል ቦታ መርጣ ገንዳው ዳር ተቀመጠችና እግራን ብቻ ውሀ ውስጥ በማስገባት ልክ መዋኘት እንደሚፈልግ … ግን ዋና ስለማይችል መግባቱን እንደፈራ ሰው በመምሰል ማንቦጫረቅ እና በእጇ እየጨለፈች በውሀው መጫወት ጀመረች….
አዎ ልጁ እየዋኘ ወደስሯ ተጠጋ…ተመልሶ ሄደ ..ሶስት አራቴ በሰሯ ተመላለሰ…በአምስተኛው በአጠገቧ ሲያልፍና በጣም ሲጠጋት…
‹‹ታድለህ ››አለችው
‹‹ምን አልሺኝ…?››
‹‹ እንደ ዓሳ ነው የምትዋኘው…ታስቀናለህ…!!! ››
‹‹አመሰግናለሁ…››ብሏት ዋናውን ሊቀጥል ካለ በኃላ መልሶ ወደ እሷ በመዞር..‹‹ለምን አትገቢም…? ››ሲል ጠየቀት
‹‹መግባት እፈልጋለሁ ..ግን ዋና አልችልም፤ ብሰምጥስ…?››
‹‹አይዞሽ እኔ እጠብቅሻለው ግቢ››
‹‹ኸረ ተው ይቅርብኝ››ተግደረደረች
‹‹ግቢ. በእኔ ተማመኚ››
የምትፈልገው ሀሳብ ስለሆነ ቀሰ ብላ ገባችና ልክ እንደጀማሪ ዋናተኛ ተንደፋደፈች..በቅርቧ ስለነበረ ቶሎ ብሎ ከስር ገባና ሰቅስቆ በክንዶቹ
መሀል አድርጎ ወደ ላይ አወጣት …
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
ኬድሮን ከምሽቱ 11 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ደባበራት እና ከቤቷ ወጣች… ቦሌ አካባቢ ወደሚገኝ ሰሞኑን ወደተከፈተ አንድ ሆቴል ነው እየሄደች ያለችው ..መኪናዋን ሆቴሉ ግቢ ውስጥ በማስገባት ምቹ ቦታ ፈልጋ አቆመችና የለበስችውን ልብስ እዛው ከመኪናዋ ሳትወርድ አወላልቃ የዋና ልብሷን በመልበስ ወደ ዋና ጋንዳው አመራች ..ሰውነቷን ጭፍግግ ስላለት ዘና ማለት ነው የፈለገችው….በዋና ሰውነቷን ማፍታታት……
የዋና ገንዳው አካባቢ እንደደረሰች ዘላ ውሀ ውስጥ ገብታ መንቦጫረቅ አልፈለገችም…የመዋኛ ገንዳውን ዙሪያ ከበው ወደ ተዘረጉ ዘመናዊ ወንበሮች ሄደችና ..ባዳውን ከሆነ አንድ ወንበር ላይ ዘና ብላ በመቀመጥ የሚዋኙትን ታዳሚዎች እያየችና እየታዘበች መዝናናቷን ቀጠለች…..
…..አበሻም ፈረንጆችም…. ሴቶችም ወንዶችም… ህፃናትም፤ ወጣትና አሮጊቶችም በስብጥር ሲዋኙ እና ሲንቦጫረቁ ይታያሉ….
ስሜቷ አንቀልቅሎ ወደ እዚህ ስፍራ ያመጣት ለምን እንደሆነ እስከአሁን አልተገለፀላትም .. …?….. ድንገት ግን ሳታስብ አንድ ወጣት ዕድሜው በግምት በ25 30 ዓመት መካከል የሚገኝ ወንድ ላይ አይኗ አረፈ…ያምራል… በጣም ነው የሚያምረው..፡፡ ከደረቱ በላይ ያለው የሰውነት ቅርጽ ውጥርጥር ያለ እና ሚማርክ ነው…ፀጉሩ በውሀው አቅም ተሸንፎ በሚመስል ሁኔታ ዝልፍልፍ ብሎ ግንባሩ ላይ ተዘናፍሏል፡፡አይኖቹ ከጨረቃ የተዋሳቸው ይመስላሉ…ኪሊማንጀሮ ተራራ ጫፍ ላይ ያገኘችውን አንድሪውን አስታወሳት፡፡.
እሷ ደግሞ ካለ ችግሯ ወይም ድክመት ሊባልም ይችላል ስድስት ወር ወይም አመት ምንም ወንድ ሳያምራት ወይም ከምንም አይነት ወንድ ጋር ሳትነካካ ትቆይና ድንገት በሰከንድ ውስጥ በእይታዋ ውስጥ የሆነ ወንድ ገብቶ ቀልቧን ከሰረቀት በቃ..ስግብግብ ነው የምትለው..፡፡በዛኑ ቀን ወይም ከተቻለም በዛኑ ደቂቃ ማግኘትና አምሮቷን መወጣት አለባት….(ያው የእሷ ፍቅር ከአንድ ጊዜ የወሲብ ፍላጎት አያልፍም ..ከዛ በላይ ፈልጋ አታውቅም ..ለእሷ በፍቅር መነሁለል እና . ወንድን እየተከተሉ መዞር ወይም ወንድ አፈቀርኩሽ እያለ ለሀጩን እያዝረበረበ በዙሪያዋ እንዲሽከረከርባት በፍፅም አትፈቅድም….)
.የእሷ ችግር ጊዜያዊ ነው ..ጊዜያዊም ብቻ ሳይሆን ቅፅበታዊም ጭምር ነው….በፈለገች ጊዜ ማግኘት አለባት… .ካለበለዛ እራሷን ሁሉ መቆጣጠር ስለሚያቅታት ጥፋት ታጠፋለች....የማይሰራ ስራ ትሰራለች…የወሲብ ጠኔም በቀላሉ አዙሮ እና አጥወልውሎ ሊደፋት ሁሉ ይችላል….እና አሁንም ይሄ ሻንቂላ ወንዳ ወንድ ወጣት እፊቷ ያለው ሰማያዊ መዋኛ ገንዳ ውስጥ ጥበባዊ በሆነ ስልት እንደ ዓሳ ነባሪ ብቅ ጥልቅ በማለት እየዋኘ ቀልቧን ስልብልብ አድርጎታል..
‹‹ተይ ይቅርብሽ››እራሷን ለመገሰፅ ሞከረች…እራሷን መገደብ እንደማይሳካላት ግን ከልምድ ታውቃለች… …..ከለበሰችው የዋና ልብስ ስር እግሯ እና እግሯ መካከል ያሳክከት ጀመረ.. እጣቷን ወደ ጭኗ መካከል በመስደድ የሚበላትን አካባቢ አከክ…አከ…ክ አድርጋ ተንፈስ ለማለት አሰበችና ዙሪያዋን በሰዎች መከበቧን ሳታስተውል መልሳ ተወችው....ከተቀመጠችበት መቀመጫ ተነሳችና ወደዋናው ገንዳ ቀረበች…ምን ማድረግ እንዳለባት እያሰበች ነው…ድንገት በትይዩ አቅጣጫ በሰማዩ ላይ በሶስት መቶ ሜትር ርቀት …. ንስራ ሲያንጃብብ ተመለከተችና
‹‹…ወይ ከመቼው ተከትሎኝ መጣ….ግን እንኳን መጣህ.››ስትል በውስጧ አጉረመረመች…. እሱን በአቅራቢያዋ በማየቷ ደስ አላት..አዎ ይሄ ቀልቧ ያረፈበትን ወጣት ከተቻለ አሁን ለመክሰስ..ካልሆነም ለእራት ለማድረስ የእሱ እርዳታ ያስፈልጋታል….ስለደካማ ጎኑ በእነዛ ሰርሳሪ አይኖቹ በማየት ካልነገረራትና በምን ሁኔታ ብትቀርበው የሀሳቧ ሊሳካ እንደሚችል መረጃውን ካላቀበላት ባሰበችው ፍጥነት ሊሰካላት አይችልም ፡፡
ደስታዋ ግን ሀሳቡን አስባ ሳትጨርስ ነው ከውስጧ በኖ የጠፋው….የንስሯን እርዳታ መጠቀም አትችልም…ምክንያቱም ይሄ ሰው ምን አልባት የማይሆን ታሪክ ካለው..ወይም አደጋኛ ሰው ከሆነ ንስሯ የሆነ ተአምር ፈጥሮ ከእሱ ጋር በምንም አይነት ተአምር እንዳትገናኝ ያደርጋታል..በምኞቷ መካከል ጣልቃ ይገባና ያጨናግፍባታል…ያ እንዲሆን ደግሞ አትፈልግም...ስለዚህ እዚህ ታሪክ ውስጥ ንስሯን አታሳትፈውም፡፡እንደዛ ወሰነች፡፡
..እንዳዛ ከሆነ ደግሞ እየበላት ያለውን በገዛ ጣቶቾ ስታክ ማደራ ነው…ፈርዶባት ደግሞ በአንዱ የተቀሰቀውን ስሜቷ በሌላ ወንድ አካክሳ ልታበርደው አትችልም…ይሄ የእሷ የሆነ ልዩ ባህሪ ነው……
ስለዚህ ይሄን ጉዳይ በራሷ መወጣት አለባት….."ንስሯን ምንም እርዳታ አልጠይቀውም….እሱ በሚዋኝበት አካባቢ እስትራቴጂካል ቦታ መርጣ ገንዳው ዳር ተቀመጠችና እግራን ብቻ ውሀ ውስጥ በማስገባት ልክ መዋኘት እንደሚፈልግ … ግን ዋና ስለማይችል መግባቱን እንደፈራ ሰው በመምሰል ማንቦጫረቅ እና በእጇ እየጨለፈች በውሀው መጫወት ጀመረች….
አዎ ልጁ እየዋኘ ወደስሯ ተጠጋ…ተመልሶ ሄደ ..ሶስት አራቴ በሰሯ ተመላለሰ…በአምስተኛው በአጠገቧ ሲያልፍና በጣም ሲጠጋት…
‹‹ታድለህ ››አለችው
‹‹ምን አልሺኝ…?››
‹‹ እንደ ዓሳ ነው የምትዋኘው…ታስቀናለህ…!!! ››
‹‹አመሰግናለሁ…››ብሏት ዋናውን ሊቀጥል ካለ በኃላ መልሶ ወደ እሷ በመዞር..‹‹ለምን አትገቢም…? ››ሲል ጠየቀት
‹‹መግባት እፈልጋለሁ ..ግን ዋና አልችልም፤ ብሰምጥስ…?››
‹‹አይዞሽ እኔ እጠብቅሻለው ግቢ››
‹‹ኸረ ተው ይቅርብኝ››ተግደረደረች
‹‹ግቢ. በእኔ ተማመኚ››
የምትፈልገው ሀሳብ ስለሆነ ቀሰ ብላ ገባችና ልክ እንደጀማሪ ዋናተኛ ተንደፋደፈች..በቅርቧ ስለነበረ ቶሎ ብሎ ከስር ገባና ሰቅስቆ በክንዶቹ
መሀል አድርጎ ወደ ላይ አወጣት …
✨ይቀጥላል✨
👍109❤12👏1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹አይዞሽ..አይዞሽ››
‹‹ያስፈራል..››
‹‹እኔ ደግፍሻለሁ… ቀስ ብለሽ ዋኚ..››እጆቹ ከስር ሲደግፈኝ በማወቅና ባለማወቅ መካከል ሆኖ አንዴ ጡቶቼን ሲጨፈልቃት..አንዴ ወደጭኑ አካባቢ ሲንሸራተት..እሷም ደግሞ ልክ እንደፕሮፌሽናል ተዋናይ ፍጽም በማስመሰል … አንዴ የፈራች መስላ አንገቱ ላይ በመጠምጠም ከሰውነቱ ስትጣበቅ..አንዴ ከእጁ ሾልካ ውሀ ውስጥ እራሷን በመድፈቅ ስትንደፋደፍ…..በመጋል እና በመቃተት መካከል ሆና ግማሽ ሰዓት ያህል ካለማመዳት በኃላ
‹‹ለዛሬ ይብቃሽ ልወጣ ነው ››አለት…
ቅፅበታዊ ውሳኔው አበሳጫት
‹‹እንዴ ምነው …?በደንብ ሳልችል…?››ኮስተር ብላ..ኮስተር አባባሎን ለተመለከተ ገንዘብ ከፍላው የሚያስተምራትን ሰው የምታወራ ነው የሚመስለው፡፡
መቼም የመልመድ ተስፋ የላትም የሚል በሚመስል ስሜት ‹‹አረ ባክሽ..!!እኛ በስንት አመትና ልፋት የቻልነውን ዋና አንቺ በአንድ ቀን ..ለዛውም በግማሽ ሰዓት መልመድ ትልጊያለሽ……?.››አላት..
የሚያወሩት በጣም ጥልቅ ያልሆነ የገንዳው ጠርዝ አካባቢ ቆመው ነው..ውሀው እሷን ጡቷ አካባቢ እሱን ደግሞ እንብርቱን አካባቢ ድረስ ሸፍኖቸዋል…ከፊል እርቃናቸውን እየታያዩ ፊት ለፊት ተፋጠው ነው የምያወሩት..እሷ ለወሲብ እየጎመዣች..እሱ በትምክት እየጎረረባት
‹‹አረ በናትህ ዋናን እኮ የተለየ ጥበብ አደረከው..›› አለችው..እወነቷን ነበር ያለችውት፡፡
እሷ የደሎ መና ልጅ ነኝ..ዋና እየተስገመገመ በሚጋልበው የያዶት ወንዝ በ3 አመቷ በቀልድ ነው የለመደችው…በዕቃ ዕቃ ጫወታ…ያዶት መዋኘት ለለመደ ሰው ደግሞ እዚህ የረጋ ወሃ ላይ መዋኘት ቀልድ ነው፡፡
‹‹እንግዲህ ጥበብ ካልሆነ ያው ሜዳው…አሳይና››ብሎ አበሳጫት…የጀመረችውን የማጥመጃ ዘዴ በደቂቃ ውስጥ እረስታ ያልሸነፍ ባይነት እና የበላይነት መንፈሷ ከውስጧ ተንቀልቅሎ ገነፈለባት…በቆመችበት ቦታ ድንገት ሰመጠችና ውስጥ ለውስጥ መሹለክለክ ጀመረች … ካለችበት ጫፍ ወደሌላ ጫፍ ተወነጨፈችና በሰካንድ በዛኛው ጫፍ ስትወጣ እሱም እሷን ፍለጋ ሰምጦ ኖሮ በድንጋጤ ከመሀከል አካባቢ ከውሀ ውስጥ ሲወጣ ተመለከተችው..አይኑን ከወዲህ ወዲያ አማተረና እሱ ካለበት በብዙ እርቀት ተስፈንጥራ ከውሀ ውስጥ በሰላም እና በፈገግታ ታጅባ ብቅ ጥልቅ እያለች ሲያያት በመገረም እና በንዴት አፈጠጠባት… በቄንጥና ቲያትራዊ በሆነ ትዕይንት ከላይ እየተንሳፈፈች ፤ እየዋኛችና እየተገለባበጠች ስሩ ደረሰች፡፡
‹‹እያሾፍሽብኝ ነበር..…?እኔ ደግሞ የሰመጥሽ መስሎኝ መደንገጤ››
‹‹ብሰምጥስ ምን ያስደነግጥሀል…?››
‹‹እንዴ ሰው አይደለሽ …? ለምን አልደነግጥ…?››
‹‹ስለተጨነክልኝ አመሰግናለሁ››
‹‹አረ ምስጋናሽን ቀቅለሽ ብይው..በአንቺ ቤት አራዳ ሆነሽ በዘዴ መጥበስሽ ነው?››
‹‹ምን ለማለት ፈልገህ ነው…?››ንግግራቸውን በቅርባቸው የነበሩ ሁለት ሰዎች የሚዋኙ መስለው ግን ጆሮቸውን ወደ እነሱ ቀስረው እያዳመጡ ነው..ደንታም አልሰጣት፡፡
‹‹ሰምተሻል ባክሽ….እኔ ለእንደአንቺ አየነት ጩሉሌ ከምሸነፍ አራሴን ባጠፋ ይሻለኛል…..
"እኔ ደግሞ በጥቂት ቀን አንተን መጥበስ ካልቻልኩ እራሴን አጠፋለሁ"
"አፍጥጦ አያትና ምንም ሳይናገር ጥሏት ሄደ
እሷም ከገንዳው ወጥታ ወደመኪናዋ ተንደረደረች...
ከፍታ ገባችና በውሀ የራሰውን የዋና ልብሷን አውልቃ ሌላ ልብሷን በመልበስ ከመኪናው ወጣች..ኮፈኑን ተደግፋ ንስሯ ፊት ለፊት ቆማ ማሰብ ጀመረች …. በአካባቢው የሚያልፍ ሰዎች ከንስር ጋር ባልተለመደ ሁኔታ ፊት ለፊት ተፋጣ ሲያዩት በመገረም እየተገላመጡ ሲያልፍ አስተውላለች፡፡
‹‹የሆነውን አይተሀል አይደል…?በቃ ፈልገዋለሁ››የምታወራው ለንስሯ ነው
(ይቅርብሽ የሚል ቃል ወደ አዕምሮዋ ላከላት)
‹‹ አታበሳጨኝ..በቃ ፈለኩት ማለት ፈለኩት ነው …አሁን የሆነ ነገር አድርግልኝ …ሆቴሉ በረንዳ ላይ ቁጭ ብዬ ቢራ እየተጎነጨው እጠብቅሀለሁ…››
ተነስቶ በረረ……..
እሷም እንዳለችው ወደሆቴሉ በረንዳ በመሄድ ወንበር ይዛ ተቀመጠችና ቢራ አዘዘች….እንግዲህ ያሰበችው እስኪሳካ ሌላነገር ማሰብም አልቻለችም…ቀልቧን ሁሉ ጥቁሩ ልጅ ላይ እንደተጣበቀ ነው…….ጭኗ መካከል ይበላት የነበረው አሁንም እየበላት ነው…. ከመብላቱም አልፎ እያቁነጠነጣት ነው… አሁን እንደዚህ የሚያደርጋት የወሲብ ጥማት ነው…እንጂማ በቅጽበታዊ የፍቅር ፍላፃ ተመታ አይመስልም… ‹‹እንደዛ አይነት ደካማነትማ አይነካካኝም…መጀመሪያውኑስ ፍቅር ምንድነው …...?የፍቅር መነሻውም መድረሻውም አይስማማኝም፡፡ማለቴ በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል ያለው የፍቅር ስሜት መነሻው የተለያየ ቢሆንም መዳረሻው ለምን ተቀራራቢ ወይም ተመሳሳይ ሆነ….ሁል ጊዜ ለምን ፍቅር በወሲብ ልጥ ይታሰራል፡፡ልጡስ ለምን በጋብቻ ሰንሰለት እንዲቀየር ይጠበቃል?ለምን ፍቅር….ወሲብ..መለያት ወይም ፍቅር….ወሲብ ..ጋብቻ ..ልጅ መውለድ….፡፡ሌላስ አማራጭ ለምን አይኖርም…ለምሳሌ ፍቅር …ጓደኝነት….በቃ፡፡እንደዛ ቢሆን ምንም ገደብ አያጨናግፈውም…አንድ ወንድ መቶ ሴት ቢያፈቅር ሚኮንነው ሰው የለም…ምክንያቱም ፍቅር ከዛ ጓደኝነት ነው…ባል ይኑራቸው አይኑራቸው….ወደፊት ያግብ አያግቡ አያስጨንቀውም…፡፡ፍቅር ብቻ…ከልብ ማፍቀር ግን ደግሞ እንዳሻቸው ሲበሩና ሲከንፉ እያዩ መደሰት…ሲያገቡ መጨፈር..ሲወልዱ መሳም….ሲያለቅሱ ጉያ ውስጥ ሸጉጦ ማባበል፡፡ግን ይህ ህልም ብቻ ነው …አጉል ምኞት ፡፡ተፈጥሮም ማህበረሰብም አይፈቅድም፡፡ወንድ አንድን ሴት አፍቅሮ እጆቾን ሲነካ በሰውነቱ እሳተ ጎመራ ይንቀለቀላል…ከንፈሯን መገሽለጥ ጭኖቾን መፈልቀቅ ቀዳሚ ምኞቱ ይሆናል…በቃ ማህበረሰብም ተፋቀሩ ሲል ተኙ መከተል እንዳለበት ያምናል..ፍቅር እና አልጋ…ነገሩ ጥሩ ነው ጤነኝነትም ነው…ፍቅርም ወሲብም ለሰው ልጅ የተሰጡ ደስታቸውን የሚያመርቱባቸው ተፈጥሮአዊ የስሜት እርካታ ፍብሪካዎቻቸው ናቸው፡፡ግን ቢሆንስ ሁሉም ፍቅር ወደወሲብ ሁሉም ወሲብ ደግሞ ወደ ጋብቻ መቀየር አለበት ወይ… ?….አይ ምን እየቀባጠርኩ ነው …አትፍረዱብኝ ምን አልባት ይሄንን አይነት ከሰው ልጅ አስተሳሰብ ውጭ የሆነ ነገር ከአባቴ ዝርያ በደም የወረስኩት ይሆናል፡፡››በማለት ስትብሰለሰል ቆየች
ከ15 ደቂቃ በኋላ ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ንስሯ ተመልሷ መጣና በቅርብ ርቀት ጨለማውን እየሰነጠቃ በአየር ላይ ሲንሳፈፍ ተመለከተችው…ሀሳቧን ሰበሰበችና ከእሱ አእምሮው ጋር አገናኘችት… ያየችውን ወይም አሁን እያየች ያለውን ነገር ለማየት ….
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹አይዞሽ..አይዞሽ››
‹‹ያስፈራል..››
‹‹እኔ ደግፍሻለሁ… ቀስ ብለሽ ዋኚ..››እጆቹ ከስር ሲደግፈኝ በማወቅና ባለማወቅ መካከል ሆኖ አንዴ ጡቶቼን ሲጨፈልቃት..አንዴ ወደጭኑ አካባቢ ሲንሸራተት..እሷም ደግሞ ልክ እንደፕሮፌሽናል ተዋናይ ፍጽም በማስመሰል … አንዴ የፈራች መስላ አንገቱ ላይ በመጠምጠም ከሰውነቱ ስትጣበቅ..አንዴ ከእጁ ሾልካ ውሀ ውስጥ እራሷን በመድፈቅ ስትንደፋደፍ…..በመጋል እና በመቃተት መካከል ሆና ግማሽ ሰዓት ያህል ካለማመዳት በኃላ
‹‹ለዛሬ ይብቃሽ ልወጣ ነው ››አለት…
ቅፅበታዊ ውሳኔው አበሳጫት
‹‹እንዴ ምነው …?በደንብ ሳልችል…?››ኮስተር ብላ..ኮስተር አባባሎን ለተመለከተ ገንዘብ ከፍላው የሚያስተምራትን ሰው የምታወራ ነው የሚመስለው፡፡
መቼም የመልመድ ተስፋ የላትም የሚል በሚመስል ስሜት ‹‹አረ ባክሽ..!!እኛ በስንት አመትና ልፋት የቻልነውን ዋና አንቺ በአንድ ቀን ..ለዛውም በግማሽ ሰዓት መልመድ ትልጊያለሽ……?.››አላት..
የሚያወሩት በጣም ጥልቅ ያልሆነ የገንዳው ጠርዝ አካባቢ ቆመው ነው..ውሀው እሷን ጡቷ አካባቢ እሱን ደግሞ እንብርቱን አካባቢ ድረስ ሸፍኖቸዋል…ከፊል እርቃናቸውን እየታያዩ ፊት ለፊት ተፋጠው ነው የምያወሩት..እሷ ለወሲብ እየጎመዣች..እሱ በትምክት እየጎረረባት
‹‹አረ በናትህ ዋናን እኮ የተለየ ጥበብ አደረከው..›› አለችው..እወነቷን ነበር ያለችውት፡፡
እሷ የደሎ መና ልጅ ነኝ..ዋና እየተስገመገመ በሚጋልበው የያዶት ወንዝ በ3 አመቷ በቀልድ ነው የለመደችው…በዕቃ ዕቃ ጫወታ…ያዶት መዋኘት ለለመደ ሰው ደግሞ እዚህ የረጋ ወሃ ላይ መዋኘት ቀልድ ነው፡፡
‹‹እንግዲህ ጥበብ ካልሆነ ያው ሜዳው…አሳይና››ብሎ አበሳጫት…የጀመረችውን የማጥመጃ ዘዴ በደቂቃ ውስጥ እረስታ ያልሸነፍ ባይነት እና የበላይነት መንፈሷ ከውስጧ ተንቀልቅሎ ገነፈለባት…በቆመችበት ቦታ ድንገት ሰመጠችና ውስጥ ለውስጥ መሹለክለክ ጀመረች … ካለችበት ጫፍ ወደሌላ ጫፍ ተወነጨፈችና በሰካንድ በዛኛው ጫፍ ስትወጣ እሱም እሷን ፍለጋ ሰምጦ ኖሮ በድንጋጤ ከመሀከል አካባቢ ከውሀ ውስጥ ሲወጣ ተመለከተችው..አይኑን ከወዲህ ወዲያ አማተረና እሱ ካለበት በብዙ እርቀት ተስፈንጥራ ከውሀ ውስጥ በሰላም እና በፈገግታ ታጅባ ብቅ ጥልቅ እያለች ሲያያት በመገረም እና በንዴት አፈጠጠባት… በቄንጥና ቲያትራዊ በሆነ ትዕይንት ከላይ እየተንሳፈፈች ፤ እየዋኛችና እየተገለባበጠች ስሩ ደረሰች፡፡
‹‹እያሾፍሽብኝ ነበር..…?እኔ ደግሞ የሰመጥሽ መስሎኝ መደንገጤ››
‹‹ብሰምጥስ ምን ያስደነግጥሀል…?››
‹‹እንዴ ሰው አይደለሽ …? ለምን አልደነግጥ…?››
‹‹ስለተጨነክልኝ አመሰግናለሁ››
‹‹አረ ምስጋናሽን ቀቅለሽ ብይው..በአንቺ ቤት አራዳ ሆነሽ በዘዴ መጥበስሽ ነው?››
‹‹ምን ለማለት ፈልገህ ነው…?››ንግግራቸውን በቅርባቸው የነበሩ ሁለት ሰዎች የሚዋኙ መስለው ግን ጆሮቸውን ወደ እነሱ ቀስረው እያዳመጡ ነው..ደንታም አልሰጣት፡፡
‹‹ሰምተሻል ባክሽ….እኔ ለእንደአንቺ አየነት ጩሉሌ ከምሸነፍ አራሴን ባጠፋ ይሻለኛል…..
"እኔ ደግሞ በጥቂት ቀን አንተን መጥበስ ካልቻልኩ እራሴን አጠፋለሁ"
"አፍጥጦ አያትና ምንም ሳይናገር ጥሏት ሄደ
እሷም ከገንዳው ወጥታ ወደመኪናዋ ተንደረደረች...
ከፍታ ገባችና በውሀ የራሰውን የዋና ልብሷን አውልቃ ሌላ ልብሷን በመልበስ ከመኪናው ወጣች..ኮፈኑን ተደግፋ ንስሯ ፊት ለፊት ቆማ ማሰብ ጀመረች …. በአካባቢው የሚያልፍ ሰዎች ከንስር ጋር ባልተለመደ ሁኔታ ፊት ለፊት ተፋጣ ሲያዩት በመገረም እየተገላመጡ ሲያልፍ አስተውላለች፡፡
‹‹የሆነውን አይተሀል አይደል…?በቃ ፈልገዋለሁ››የምታወራው ለንስሯ ነው
(ይቅርብሽ የሚል ቃል ወደ አዕምሮዋ ላከላት)
‹‹ አታበሳጨኝ..በቃ ፈለኩት ማለት ፈለኩት ነው …አሁን የሆነ ነገር አድርግልኝ …ሆቴሉ በረንዳ ላይ ቁጭ ብዬ ቢራ እየተጎነጨው እጠብቅሀለሁ…››
ተነስቶ በረረ……..
እሷም እንዳለችው ወደሆቴሉ በረንዳ በመሄድ ወንበር ይዛ ተቀመጠችና ቢራ አዘዘች….እንግዲህ ያሰበችው እስኪሳካ ሌላነገር ማሰብም አልቻለችም…ቀልቧን ሁሉ ጥቁሩ ልጅ ላይ እንደተጣበቀ ነው…….ጭኗ መካከል ይበላት የነበረው አሁንም እየበላት ነው…. ከመብላቱም አልፎ እያቁነጠነጣት ነው… አሁን እንደዚህ የሚያደርጋት የወሲብ ጥማት ነው…እንጂማ በቅጽበታዊ የፍቅር ፍላፃ ተመታ አይመስልም… ‹‹እንደዛ አይነት ደካማነትማ አይነካካኝም…መጀመሪያውኑስ ፍቅር ምንድነው …...?የፍቅር መነሻውም መድረሻውም አይስማማኝም፡፡ማለቴ በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል ያለው የፍቅር ስሜት መነሻው የተለያየ ቢሆንም መዳረሻው ለምን ተቀራራቢ ወይም ተመሳሳይ ሆነ….ሁል ጊዜ ለምን ፍቅር በወሲብ ልጥ ይታሰራል፡፡ልጡስ ለምን በጋብቻ ሰንሰለት እንዲቀየር ይጠበቃል?ለምን ፍቅር….ወሲብ..መለያት ወይም ፍቅር….ወሲብ ..ጋብቻ ..ልጅ መውለድ….፡፡ሌላስ አማራጭ ለምን አይኖርም…ለምሳሌ ፍቅር …ጓደኝነት….በቃ፡፡እንደዛ ቢሆን ምንም ገደብ አያጨናግፈውም…አንድ ወንድ መቶ ሴት ቢያፈቅር ሚኮንነው ሰው የለም…ምክንያቱም ፍቅር ከዛ ጓደኝነት ነው…ባል ይኑራቸው አይኑራቸው….ወደፊት ያግብ አያግቡ አያስጨንቀውም…፡፡ፍቅር ብቻ…ከልብ ማፍቀር ግን ደግሞ እንዳሻቸው ሲበሩና ሲከንፉ እያዩ መደሰት…ሲያገቡ መጨፈር..ሲወልዱ መሳም….ሲያለቅሱ ጉያ ውስጥ ሸጉጦ ማባበል፡፡ግን ይህ ህልም ብቻ ነው …አጉል ምኞት ፡፡ተፈጥሮም ማህበረሰብም አይፈቅድም፡፡ወንድ አንድን ሴት አፍቅሮ እጆቾን ሲነካ በሰውነቱ እሳተ ጎመራ ይንቀለቀላል…ከንፈሯን መገሽለጥ ጭኖቾን መፈልቀቅ ቀዳሚ ምኞቱ ይሆናል…በቃ ማህበረሰብም ተፋቀሩ ሲል ተኙ መከተል እንዳለበት ያምናል..ፍቅር እና አልጋ…ነገሩ ጥሩ ነው ጤነኝነትም ነው…ፍቅርም ወሲብም ለሰው ልጅ የተሰጡ ደስታቸውን የሚያመርቱባቸው ተፈጥሮአዊ የስሜት እርካታ ፍብሪካዎቻቸው ናቸው፡፡ግን ቢሆንስ ሁሉም ፍቅር ወደወሲብ ሁሉም ወሲብ ደግሞ ወደ ጋብቻ መቀየር አለበት ወይ… ?….አይ ምን እየቀባጠርኩ ነው …አትፍረዱብኝ ምን አልባት ይሄንን አይነት ከሰው ልጅ አስተሳሰብ ውጭ የሆነ ነገር ከአባቴ ዝርያ በደም የወረስኩት ይሆናል፡፡››በማለት ስትብሰለሰል ቆየች
ከ15 ደቂቃ በኋላ ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ንስሯ ተመልሷ መጣና በቅርብ ርቀት ጨለማውን እየሰነጠቃ በአየር ላይ ሲንሳፈፍ ተመለከተችው…ሀሳቧን ሰበሰበችና ከእሱ አእምሮው ጋር አገናኘችት… ያየችውን ወይም አሁን እያየች ያለውን ነገር ለማየት ….
✨ይቀጥላል✨
👍130❤16😁5😱4👎3🔥1🤔1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ሰውዬው አሁን ያለበት ቦታ ከዚህ እሷ ካለችበት ብዙም በማይርቅ ሌላ ሆቴል ውስጥ ነው..ግን እየጠጣ አይደለም..ቤርጎ ውስጥ ሆኖ ነው የሚታያት፡፡ደግሞ ብቻውን አይደለም..አንድ ቅንጥስጥስ ያለች ለጋ ወጣት ክንዱ ላይ ተዘርራ በፀጉር የተሸፈነ ጥቁር ደረቱን እየዳበሰችለት ነው…..እሱ ከወገቡ በታች ቢጃማ ሱሪ አድርጓል… ልጅቱ ግን በፓንት ብቻ ነች…ደግሞ የሰውነታቸው ቀለም ልዩነት ..እሷ ብጭጭ ያለች ክልስ የምትመስል ሴት ነች….ደግሞ ስዕል የመሰለ ውበት ያለት..
‹‹ይህቺን ይዘህ ነው ለካ በእኔ ላይ የጎረርክብኝ?››ስትል አሰበች....እና ይበልጥ የፉክክር መንፈሷ ተነቃቃ…
‹‹የእኔ ፍቅር አሁንም እንደተበሳጨህ ነው?››ልጅቷ ነች የጠየቀችው
‹‹በጣም እኮ የምታናድድ ሴት ነች..አንተን በዛሬው ቀን ካላወጣሁ እራሴን አጣፋለሁ ትለኛለች?››
(አሁንም ስለእሷ እያወራ መሆኑን ስታውቅ ውስጧ ሞቀ..የሚበላት አካባቢም ጨመረ)
‹‹ታዲያ ጤነኛ ነች ትላለህ?››
‹‹ጤነኛማ አይደለችም››
‹‹ታዲያ ንቀህ ተዋታ..ለምን አትረሳትም .... ?መቼስ አሁን እኔ እቅፍ ውስጥ ነህ…መጠጡም እዚሁ ክፍላችን አለ.. እራቱም እዚሁ ነው የሚመጣልን..እኔን የመሰለች ዘበኛ አለህ እንዴት ብላ ከየት ታገኝሀለች..ነው ወይስ እንደፎከረችው እራሷን ታጠፋለች ብለህ ሰጋህ?››
‹‹ፍግም ትበላ››
‹‹ተው ተው እደዛማ አይባልም…አሁን ለሚሰማህ ሰው አሪፍ ጨካኝ አትመስልም…ሁል ጊዜ እኮ አንደበትህ እና ሆድህ አይገናኝም……….››
‹‹እና እንዴት ነው የሚባለው?››
‹‹አይ ያን ያህል ከወደደችህማ እራሷን ከምታጠፋ አንዴ ብትቸገርላት?››
ገፍትሮ ከደረቱ ላይ አስፈነጠራት ..
እየሳቀች ‹‹አትበሳጭ.. ቀልዴን እኮ ነው›› አለችው ወደአስለቀቃት ቦታ እየተመለሰች
‹‹እንዲህ አይት ቀልድ አይመቸኝም ..ካንቺ ውጭ የሌላ ሴት ገላ ከማቀፍ እኔም እራሴን ባጠፋ ይሻለኛል…››
‹‹በቃ የእኔ ጀግና›› ብላ ወደ ደረቱ ተመለሰችና ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት… ገለበጣትና እላዬ ላይ ተከመረባት…መሳሙን ሳያቆም በአንድ እጁ የለበሰውን ቢጃማ ከሰውናቱ መዥርጦ አወለቀ..
በንስራ ታግዛ እያየችው ያለው ገበናቸው የወሲብ ረሀቧን ከምትቆጣጠረው በላይ እንዲሆንባት አደረገው ፡፡
እሷ ልትተኛው የፈለገችው ወንድ ከዕጮኛው ጋር በወሲብ ዳንኪራ እየጨፈረ ነው…እናም ደግሞ በራሱ ታማኝነት እንዴት ተመፃዳቂ እንደሆነ ከንግግሩ ለሁለተኛ ጊዜ መስማቷ የቅድሞውን ብስጭቷን በእጥፍ እንዲጨምር አደረገው…
ሂሳቧን ከፈለችና መቀመጫዋን ለቃ ወደመኪናዋ አመራች ..መኪናዋን አስነሳችና ሰውዬዋ ወዳረፈበት ሆቴል ነዳችው… ንስሯም በሰማዩ ላይ ጭለማውን ሰማይ እየሰነጠቀ ከላይ እየተከተላት ነው፡፡
ንስሯ‹‹ፍቅራቸውን እና መተማመናቸውን አየሽ አይደል…?ተይው በቃ….››የሚል መልዕክት አስተላለፈላት
‹‹አልተውም.. የማታግዘኝ ከሆነ በራሴ እወጣዋለሁ….››መለሰችለት ለንስሯ
‹‹በራስሽማ የበለጠ ጥፋት ታጠፊያለሽ››
‹‹እንግዲያው ዝም ብለህ በቀላሉ ያሰብኩትን እንደሳካ አግዘኛ››
ንስሩ የመስማማት ምልክት አሳያት ..
አሁን ሆቴል ደረሰችና መኪናዋን ቦታ አስይዛ አቆመችና ሞተሩን አጠፋች ….በቀጣይ ምታደርገውን ነገር ግን ገና አላወቀችውም .. መኪናዋ ውስጥ ሆና ትኩረቷን ስብስባ እና ከንስሯ እይታ ጋር እይታዋን በማጣመር ልክ ለስለላ በድብቅ እንደተቀበረ ካሜራ ክፍላቸውን ወደመቃኘቱ ተመሰች
አሁን ፍቅረኛሞቹ ስራቸውን ጨርሰው ሻወር ቤት ግብተዋል…እየታጠቡ ነው ፡፡በመታጠባቸው ውስጥ መተሸሻት ..በመተሻሸታቸው ውስጥ ከወሲባዊ እርካታ በኃላ ያለ ድሪያ አይነት ማሽካካት ይታይባቸዋል….. ታጥበው ከጨረሱ በኃላ ሁለቱም ፎጣ አገልድመው ሻወሩን ለቀው በመውጣት አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አሉ….እሱ ተንጠራራና ፊት ለፊታቸው ካለው ጠራጴዛ የወይን ጠርሙሱን በማንሳት የጎደለውን የወይን ብረጭቆ በመሙላት አንስቶ ሰጣት ..ለራሱም አነሳና ተጎነጨ ….እሷ ግን ጠቀም አድርጋ ተጎነጨችና አፏን ወደእሱ አሞጠሞጠች …ከፈተላት.. በጉንጮቾ ያቆረችውን ወይን በከፈተላት ጉንጩ ውስጥ ገለበጠችለት››ይሄንን ስታይ የሆነ ምቾቷ እየቀነሰ መጣ….ያልተለመደ አይነት ሆነባት፡፡
‹‹አሁን ሰርጋችን ቀን መቼ እናድርገው?››እሱ ነው አይን አይኗን በስስት እያያት የጠየቀው፡፡
‹‹እኔ እንጃ››
‹‹በእኔ በኩል በጣም በቅርብ መሆን አለበት ባይ ነኝ››
‹‹ቅርብ ስትል? ››
‹‹በሚቀጥለው ወር ውስጥ››
‹‹እርግጠኛ ነህ….?እኔ ግን ያለችንን ጊዜ እንደዚሁ በፍቅር ብናሳልፋት ይሻል ይመስለኛል፡፡
‹‹አንቺ ደግሞ ስንት ወር ያወራንበትን ነገር ከእንደገና ወደኃላ ትመልሺዋለሽ ..አድሮ ቃሪያማ አትሁኚ››ኮስተር ብሎ መለሰላት
‹‹የእኔ ፍቀር ላንተው እኮ አስቤ ነው…ከዚህ ጋብቻ መሳቀቅ ብቻ ነው የሚተርፍህ ››
ያንን ጥቁር ፊቱን ይበልጥ አጨልሞ ‹‹ግድ የለም ለእኔ አታስቢ..አንቺ ባለችሽ ጊዜ ቶሎ ቶሎ መኖር መቻል አለብሽ ፡፡.ድል ባለ ሰርግ ማግባት …ልጅ ወልዶ ማቀፍና ማጥባት ላንቺ የሚገቡሽ ነገሮች ናቸው››አላት
‹‹ትቀልዳለህ…..ከዚህ በፊትም ነግሬሀለው …ዛሬም እንደግምልሀለው የማላሳድገውን ልጅ በፍጽም አልወልድም››
‹‹እንግዲህ ነግሬሻለሁ…
ካልወለድሽልኝ አንቺ ጥለሺኝ ስትሄጂ የምጽናናበት ነገር ስለሌለ ያው ከሸኘሁሽ በኃላ እራሴን በማጥፋት እንደምከተልሽ እና በምትቀበሪበት ጉድጓድ አብሬሽ እንደምቀበር አትጠራጠሪ››
‹‹ለምን ታስጨንቀኛለህ?››
‹‹እያስጨነቅኩሽ አይደለም…በትክክል የማደርገውን እየነገርኩሽ ነው…አንቺ ስለመሞትሽ ማሰብን እርሺውና በየቀኑ ማድረግ የምንችለውን እናድርግ.. እንጋባ… ውለጂልኝ..ከዛ በኃላ ያለውን ነገር ለእግዜር እንተወው ..ምን ይታወቃል የሆነ ተአምር ተፈጥሮ በሀኪም ከተቆረጠው የመሞቻ ቀንሽ በፊት ፈውስ የሚሆን መድሀኒት ይገኝ ይሆናል››
ኬድሮን በምሰማው ነገር እየደነዘዘች ነው።
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ሰውዬው አሁን ያለበት ቦታ ከዚህ እሷ ካለችበት ብዙም በማይርቅ ሌላ ሆቴል ውስጥ ነው..ግን እየጠጣ አይደለም..ቤርጎ ውስጥ ሆኖ ነው የሚታያት፡፡ደግሞ ብቻውን አይደለም..አንድ ቅንጥስጥስ ያለች ለጋ ወጣት ክንዱ ላይ ተዘርራ በፀጉር የተሸፈነ ጥቁር ደረቱን እየዳበሰችለት ነው…..እሱ ከወገቡ በታች ቢጃማ ሱሪ አድርጓል… ልጅቱ ግን በፓንት ብቻ ነች…ደግሞ የሰውነታቸው ቀለም ልዩነት ..እሷ ብጭጭ ያለች ክልስ የምትመስል ሴት ነች….ደግሞ ስዕል የመሰለ ውበት ያለት..
‹‹ይህቺን ይዘህ ነው ለካ በእኔ ላይ የጎረርክብኝ?››ስትል አሰበች....እና ይበልጥ የፉክክር መንፈሷ ተነቃቃ…
‹‹የእኔ ፍቅር አሁንም እንደተበሳጨህ ነው?››ልጅቷ ነች የጠየቀችው
‹‹በጣም እኮ የምታናድድ ሴት ነች..አንተን በዛሬው ቀን ካላወጣሁ እራሴን አጣፋለሁ ትለኛለች?››
(አሁንም ስለእሷ እያወራ መሆኑን ስታውቅ ውስጧ ሞቀ..የሚበላት አካባቢም ጨመረ)
‹‹ታዲያ ጤነኛ ነች ትላለህ?››
‹‹ጤነኛማ አይደለችም››
‹‹ታዲያ ንቀህ ተዋታ..ለምን አትረሳትም .... ?መቼስ አሁን እኔ እቅፍ ውስጥ ነህ…መጠጡም እዚሁ ክፍላችን አለ.. እራቱም እዚሁ ነው የሚመጣልን..እኔን የመሰለች ዘበኛ አለህ እንዴት ብላ ከየት ታገኝሀለች..ነው ወይስ እንደፎከረችው እራሷን ታጠፋለች ብለህ ሰጋህ?››
‹‹ፍግም ትበላ››
‹‹ተው ተው እደዛማ አይባልም…አሁን ለሚሰማህ ሰው አሪፍ ጨካኝ አትመስልም…ሁል ጊዜ እኮ አንደበትህ እና ሆድህ አይገናኝም……….››
‹‹እና እንዴት ነው የሚባለው?››
‹‹አይ ያን ያህል ከወደደችህማ እራሷን ከምታጠፋ አንዴ ብትቸገርላት?››
ገፍትሮ ከደረቱ ላይ አስፈነጠራት ..
እየሳቀች ‹‹አትበሳጭ.. ቀልዴን እኮ ነው›› አለችው ወደአስለቀቃት ቦታ እየተመለሰች
‹‹እንዲህ አይት ቀልድ አይመቸኝም ..ካንቺ ውጭ የሌላ ሴት ገላ ከማቀፍ እኔም እራሴን ባጠፋ ይሻለኛል…››
‹‹በቃ የእኔ ጀግና›› ብላ ወደ ደረቱ ተመለሰችና ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት… ገለበጣትና እላዬ ላይ ተከመረባት…መሳሙን ሳያቆም በአንድ እጁ የለበሰውን ቢጃማ ከሰውናቱ መዥርጦ አወለቀ..
በንስራ ታግዛ እያየችው ያለው ገበናቸው የወሲብ ረሀቧን ከምትቆጣጠረው በላይ እንዲሆንባት አደረገው ፡፡
እሷ ልትተኛው የፈለገችው ወንድ ከዕጮኛው ጋር በወሲብ ዳንኪራ እየጨፈረ ነው…እናም ደግሞ በራሱ ታማኝነት እንዴት ተመፃዳቂ እንደሆነ ከንግግሩ ለሁለተኛ ጊዜ መስማቷ የቅድሞውን ብስጭቷን በእጥፍ እንዲጨምር አደረገው…
ሂሳቧን ከፈለችና መቀመጫዋን ለቃ ወደመኪናዋ አመራች ..መኪናዋን አስነሳችና ሰውዬዋ ወዳረፈበት ሆቴል ነዳችው… ንስሯም በሰማዩ ላይ ጭለማውን ሰማይ እየሰነጠቀ ከላይ እየተከተላት ነው፡፡
ንስሯ‹‹ፍቅራቸውን እና መተማመናቸውን አየሽ አይደል…?ተይው በቃ….››የሚል መልዕክት አስተላለፈላት
‹‹አልተውም.. የማታግዘኝ ከሆነ በራሴ እወጣዋለሁ….››መለሰችለት ለንስሯ
‹‹በራስሽማ የበለጠ ጥፋት ታጠፊያለሽ››
‹‹እንግዲያው ዝም ብለህ በቀላሉ ያሰብኩትን እንደሳካ አግዘኛ››
ንስሩ የመስማማት ምልክት አሳያት ..
አሁን ሆቴል ደረሰችና መኪናዋን ቦታ አስይዛ አቆመችና ሞተሩን አጠፋች ….በቀጣይ ምታደርገውን ነገር ግን ገና አላወቀችውም .. መኪናዋ ውስጥ ሆና ትኩረቷን ስብስባ እና ከንስሯ እይታ ጋር እይታዋን በማጣመር ልክ ለስለላ በድብቅ እንደተቀበረ ካሜራ ክፍላቸውን ወደመቃኘቱ ተመሰች
አሁን ፍቅረኛሞቹ ስራቸውን ጨርሰው ሻወር ቤት ግብተዋል…እየታጠቡ ነው ፡፡በመታጠባቸው ውስጥ መተሸሻት ..በመተሻሸታቸው ውስጥ ከወሲባዊ እርካታ በኃላ ያለ ድሪያ አይነት ማሽካካት ይታይባቸዋል….. ታጥበው ከጨረሱ በኃላ ሁለቱም ፎጣ አገልድመው ሻወሩን ለቀው በመውጣት አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አሉ….እሱ ተንጠራራና ፊት ለፊታቸው ካለው ጠራጴዛ የወይን ጠርሙሱን በማንሳት የጎደለውን የወይን ብረጭቆ በመሙላት አንስቶ ሰጣት ..ለራሱም አነሳና ተጎነጨ ….እሷ ግን ጠቀም አድርጋ ተጎነጨችና አፏን ወደእሱ አሞጠሞጠች …ከፈተላት.. በጉንጮቾ ያቆረችውን ወይን በከፈተላት ጉንጩ ውስጥ ገለበጠችለት››ይሄንን ስታይ የሆነ ምቾቷ እየቀነሰ መጣ….ያልተለመደ አይነት ሆነባት፡፡
‹‹አሁን ሰርጋችን ቀን መቼ እናድርገው?››እሱ ነው አይን አይኗን በስስት እያያት የጠየቀው፡፡
‹‹እኔ እንጃ››
‹‹በእኔ በኩል በጣም በቅርብ መሆን አለበት ባይ ነኝ››
‹‹ቅርብ ስትል? ››
‹‹በሚቀጥለው ወር ውስጥ››
‹‹እርግጠኛ ነህ….?እኔ ግን ያለችንን ጊዜ እንደዚሁ በፍቅር ብናሳልፋት ይሻል ይመስለኛል፡፡
‹‹አንቺ ደግሞ ስንት ወር ያወራንበትን ነገር ከእንደገና ወደኃላ ትመልሺዋለሽ ..አድሮ ቃሪያማ አትሁኚ››ኮስተር ብሎ መለሰላት
‹‹የእኔ ፍቀር ላንተው እኮ አስቤ ነው…ከዚህ ጋብቻ መሳቀቅ ብቻ ነው የሚተርፍህ ››
ያንን ጥቁር ፊቱን ይበልጥ አጨልሞ ‹‹ግድ የለም ለእኔ አታስቢ..አንቺ ባለችሽ ጊዜ ቶሎ ቶሎ መኖር መቻል አለብሽ ፡፡.ድል ባለ ሰርግ ማግባት …ልጅ ወልዶ ማቀፍና ማጥባት ላንቺ የሚገቡሽ ነገሮች ናቸው››አላት
‹‹ትቀልዳለህ…..ከዚህ በፊትም ነግሬሀለው …ዛሬም እንደግምልሀለው የማላሳድገውን ልጅ በፍጽም አልወልድም››
‹‹እንግዲህ ነግሬሻለሁ…
ካልወለድሽልኝ አንቺ ጥለሺኝ ስትሄጂ የምጽናናበት ነገር ስለሌለ ያው ከሸኘሁሽ በኃላ እራሴን በማጥፋት እንደምከተልሽ እና በምትቀበሪበት ጉድጓድ አብሬሽ እንደምቀበር አትጠራጠሪ››
‹‹ለምን ታስጨንቀኛለህ?››
‹‹እያስጨነቅኩሽ አይደለም…በትክክል የማደርገውን እየነገርኩሽ ነው…አንቺ ስለመሞትሽ ማሰብን እርሺውና በየቀኑ ማድረግ የምንችለውን እናድርግ.. እንጋባ… ውለጂልኝ..ከዛ በኃላ ያለውን ነገር ለእግዜር እንተወው ..ምን ይታወቃል የሆነ ተአምር ተፈጥሮ በሀኪም ከተቆረጠው የመሞቻ ቀንሽ በፊት ፈውስ የሚሆን መድሀኒት ይገኝ ይሆናል››
ኬድሮን በምሰማው ነገር እየደነዘዘች ነው።
✨ይቀጥላል✨
👍110❤9😱5🥰1👏1😢1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ብርጭቆውን አንስታ ተጎነጨችለትና መልሳ በማስቀመጥ መልስ ለመሰጠት ተዘጋጀች….
ኬድሮን በምታየው ነገር በጣም ደንዝዛለች …አላማዋንም ዘንግታ ….የሚበላትንም ነገር ችላ ብላ በምስጠት እየተከታተለችው ነው..በሌላ እይታ…. በሌላ መነጽር
ቀጠለች ልጅቷ‹‹የእኔ ፍቅር በጣም እኮ ነው የምትገርመኝ…. ዛሬም ተስፋ አትቆርጥም፡፡ በቃ እኔን እኮ ከዚህ በሽታዬ ለማዳን ለአመታት ለፋህ..ያለህን ንብረት ጨረስክ ..እስራኤል፤ህንድ፤አሜሪካም ጭምር ወስደህ በአለምአቀፍ ደራጃ አሉ በተባሉ የህክምና ተቋምና ምርጥ ጠቢቦች እድታከም አድርገሀል…በቃ አልተሳካም …እንደውም በአንተ ጥረት ነው የአንድ እና የሁለት አመት ቀሪ እድሜ ማግኘት የቻልኩት..ስለዚህ ይህቺን ባንተ ጥረት ያገኘኋትን ቀሪ ዕድሜዬን እንዳልከው በፍቅር እናጣጥምና ከዛ በሰላም ሸኘኝ …ባይሆን እዛ ጎጆ ቀይሼ መኖሪያ ቦታ አመቻችታ እጠብቅሀላሁ..››አለችና ጉንጩን በመሳም ስሩ ውሽቅ አለችበት..እሱም አጥብቆ አቀፋትና በአንድ እጁን ከአይኖቹ ሚንጠባጠበውን እንባ ማበስ ጀመረ ..
ከዚህ በላይ መቆየትም ሆነ በአላማዋ መግፋት አልቻለችም ….መኪናዋን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው..ተቀጣጥሎ የነበረው የወሲብ ስሜቷ አሁን ከስሟል.‹‹.በዚህ አይነት ፍቅር ውስጥ እንዴት መግባት እችላለሁ?››..ይህቺንስ ሞት ፊት ለፊቷ የቆመባትን ሴት እንዴት መፎካከር ይቻላል… ?ከእሷ መንጠቅ ወይም መስረቅ በየትኛው ሞራል….?
እንደውም ከዚህ በላይ ታሪካቸውን ማወቅ ፈለገች..ልታግዛቸው ፡፡ከቻለች ለመሞከር….ግን ዛሬ አይደለም… ሌላ ቀን …በዚህን ሰዓት በዚህ የጨፈገገ ስሜቷ ውስጥ ሆና ምንም ማድረግ አልቻለችም..አሁን እቤቷ ገብታ ጥቅልል ብላ መተኛት ብቻ ነው የምትፈልገው…መኪናዋን እያከነፈች ነው… ንስሯ ክንፉን እያርገፈገፈ ጨለማውን በመሰንጠቅ ከፊቷ ይከንፋል..ሁኔታው የደስታ ነው….መጀመሪያም አካሄዷ ደስ አላሰኘውም ነበር….ሀሳቧን ቀይራ በቁዘማም ቢሆን ወደቤቷ መመለሷ እሱን እያስፈነጠዘው ነው…፡፡
""""
ምቾት የሌላው ምሽት ነበር ያሳለፈችው….ደግሞ ርዝመቱ እንደተለመደው 11 ሰዓት ከእንቅልፏ ተነሳችና እቤቷ ውሰጥ የተወሰነ የሰውነት እንቅስቃሴ ከሰራች በኃላ ወደበረንዳዋ ወጣች…ንሰሯ አብሯት ነበር የወጣው…..ለተወሰነ ደቂቃ ሀሳቧን ከራሷ ጋር ነበር ያደረገችው.. ኤርፎኗን ጆሮዋ ላይ ሰክታ ከሞባይሏ ለስለስ ያለ ሙዚቃ ከፍተችና እያዳመጠች ንጽህ የጥዋት አየር ወደ ሳንባዋ እየማገች ነው፡፡
ግን በመረጋጋት ውስጥ ሆና በጽሞና ሙዚቃውን ብቻ ማዳመጡን ቡዙም ልትዘልቀበት አልቻለችም..ሀሳቧ አሁንም ትናንት ላይ እንደተጣበቀ ነው…የብልቷ መብላት ቢተዋትም አዕምሮዋ ግን አሁንም ድረስ እያሳከከት ነው….እሷ እኮ ወንድ ልጅን ለዚህን ያህል ጊዜ ርዝመት በልቧ አዝላ አታውቅም… ፎክራ ስላላሳካችው ዝታ ስላልፈፀመች የመሸነፍ ቁጭት የፈጠረባት መብሰልሰል ይሆናል……….?
አዎ ከንስር ጋር እየኖሩ ሽንፈትን አሜን ብሎ በመቀበል አንገትን መድፋት የማይታሰብ ነው…በምክንያቱም ለንስር መታገል.. ታግሎም ማሸነፍ ተፈጥሮ ያደለው የብቻ ፀጋቸው ነው…ንስር የሞተ እንስሳ ንክች አያደርግም…የሚገድለውን ለማጥመድ ወይም ኢላማውን ለማግኘት መቶ ኪሎ ሜትር ሊያስስ ይችላል ..አስሶ አንዴ ራዳር ውስጥ ካስገባ ግን ንቅንቅ አይልም..ምንም ተአምር አያዘናጋውም…ግዳዩን ሳይጥል ውልፍች የለም…አዎ አድኖ አሳዶና ታግሎ በመጣል የገደለውን ብቻ ነው የሚበላው….፡፡እይታው ጠሊቅና እሩቅ ነው፡ካአለበት ቆሞ በአምስት ኪሎ ሜተር እርቀት ያለ ነገር ላይ ማነጣጠር ይችላል፡፡ልፋቱ የሌለበትን… አሸናፊነቱ የማይዘመርበትን ንክች አያደርግም… …ይህ የሰው ልጅም የህይወት መስመሩን ለማግኘት የተፈጠረበትን አለማ ለመገንዘብ የእድሜውን እሩብ ሊያባክን ይችላል…. ማባከኑም አግባብ ነው..መስመሩን ከያዘ በኃላ ግን አይኑም ቀልቡም መቶ ፐርሰንት መስመሩ ላይ መሆን አለበት፡፡ ትኩረቱም ጥረቱም ወደዛ ወደህይወት ግብ መዳረሻው የሚያደርሰው ሊሆን ይገባል…. የንስር ህይወት ይሄንን ነው የሚያስተምረው…
እሷም የሰለጠንችው በንስራ ስለሆነ ኢላማ ያደረገችበትን ነገር ከግብ ካላደረሰች ያማታል….አሁን እየተሰማት ያለው ስሜት ግን የተለየ ይመስላታል … ምክንያቱም ከባሪያው ልጅ ባልተናነሰ ቀዮ እጮኛውንም ከምናቧ ልታስወግዳት አልተቻለትም፡፡
‹‹አዎ መሞት የለባትም….በዚህ ዕድሜዋ መሞት አይገባትም››…ብላ በውስጧ ደመደመች…መልሳ ደግሞ እራሷን ሞገተች፡፡
‹‹ …በዚህ ዕድሜዋ መሞት የለባትም ስል ምን ማለቴ ነው..
…….?ሰው በስንት አመቱ ነው መሞት ያለበት……….?››ስትል አሰበች፡፡
ወጣት ሆኖ የሞተ ሰው ለምን በዛ ዕድሜዬ ሞትኩ ብሎ ይቆጫል ወይም ፈጣሪውን ይወቅሳል….? አይመስለኝም፡፡.ምን አልባት ይሄኛው አለም እና ከሞት ወዲያ ያለው ያኛው አለም ተብሎ ሚከፈል ዓለም ያለ ቢሆን እንኳን ያኛው አለም በእግዜር ሙሉ ቁጥጥር እና ፍቃድ የሚተዳደር ነው ሚሆነው..እንደዛ ከሆነ ደግሞ ከዚህኛው ዓለም ፍጽም የተሻለ ነው የሚሆነው..ያ ማለት ደግሞ ሞቶ ወደዛኛው አለም የተሸጋገረ ሰው በህፃንነቱም ሆነ በወጣትነቱ ቢሄድ ተገላገልኩ በምድር ከመሰቃየት፤ከመራብ፤ከመጠማት፤ከመጋዝና ከመታሰር እንኳንም በጊዜ ወደዚህ መጣሁ የሚል ይመስለኛል፡፡ሞት ማለት ሙሉ በሙሉ በስጋ መበስበስ እና በነፍስ መክሰም ወይም ወደ ምንምነትም መቀየር ከሆነ ደግሞ ለመፀፀት እና ለምን ቶሎ ሞትኩ …….?ብሎ ለማሰብም የሚያስችል ዕድልም አይኖርም ….ሞች በቋሚው አዕምሮ ሲመዘን ነው በልጅነቱ ተቀጨ..በወጣትነቱ ተቀጠፈ የሚባለው….እና አሁንም እሷ የልጅቷ እሞታለሁ ማለት ለምን ይሄን ያህል እንዳሳሰባት አልገባትም .. …….?ነው ወይስ ለተመኘችው ልጅ ስትል ይሆናል..…….?
‹‹እሱ እንዲያዝንብኝ ስላልፈለኩ ይሆን….?››ስትል እራሷን ትጠይቃለች ..ለጠየቀችው መልስ ከመፈለግ ይልቅ ግን ሌላ ጥያቄ እየጨመረችበት ነው….
እሷ እንደሆነ በመግደልም ሆነ በማዳን አታምንም…እንደእሷ እምነት ሰው የኖረበትን ጊዜ አጭርም ሆነ ረጅም ዋናው የኖረውን ያህል ተደስቶ መኖሩ ነው…..እርግጥ መግደል የእግዜያብሄር የአታድርግ ክልከላ ውስጥ ከሚካተቱ ትዕዛዞች መካከል አንዱ እንደሆነ ታውቃለች፡፡ቢሆንም ህይወት ከመግደልና ከመገደል ውጭ ህልውናዋ ፀንቶ እንደማይቆምም በተግባር አይታለች….ብዙ መግደል የቻለ ብዙ ይኖራል….ለመግደል የሰነፈ በጠንካራው ተገድሎ በሞቱ ለሌላው መኖር ምክንያት ሆኖ ያልፋል፡፡ይሄንን ከህይወት ተምራለች፡፡
ግን እግዚያብሄር አትግደል ሲል ለሰው ብቻ ነው እንዴ የሚሰራው..…….?ሰውን መግደል ብቻ ነው በኃጥያት የሚያስጠይቀው….? ለምን ….?ሰው በእግዜያብሄር ሀምሳል ስለተፈጠረ ልዩ መብት ስላለው….?፡፡ነው ወይስ ሰው የእግዜያብሄር ቤተ መቅደስ ነው የእግዜያብሄርን ቤተ መቅደስ ማፍረስ ደግሞ ያው ቀጥታ እሱን መዳፈር ነው…..ከእሱ ጋር መላተም ነው……ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ ተብሎ ስለሚታሰብ…..? …አትግደል የተባለው ነፍስ ያለውን ሁሉ ከሆነስ ……….?ያማ የማይቻል ከባድ ትዕዛዝ ይሆናል…፡፡ምክንያቱም እንስሳት ነፍስ አላቸው… ተክሎች ነፍስ አላቸው…ለመኖር ደግሞ ህይወት ያለው ነገር ሁሉ መመገብ አለበት..ለመመገብ ደግሞ አንዱ ዝርያ ሌላውን እየበላ ነው ነፍሱን የሚያቆየው…ለመብላት ደግሞ የግድ መግደል
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ብርጭቆውን አንስታ ተጎነጨችለትና መልሳ በማስቀመጥ መልስ ለመሰጠት ተዘጋጀች….
ኬድሮን በምታየው ነገር በጣም ደንዝዛለች …አላማዋንም ዘንግታ ….የሚበላትንም ነገር ችላ ብላ በምስጠት እየተከታተለችው ነው..በሌላ እይታ…. በሌላ መነጽር
ቀጠለች ልጅቷ‹‹የእኔ ፍቅር በጣም እኮ ነው የምትገርመኝ…. ዛሬም ተስፋ አትቆርጥም፡፡ በቃ እኔን እኮ ከዚህ በሽታዬ ለማዳን ለአመታት ለፋህ..ያለህን ንብረት ጨረስክ ..እስራኤል፤ህንድ፤አሜሪካም ጭምር ወስደህ በአለምአቀፍ ደራጃ አሉ በተባሉ የህክምና ተቋምና ምርጥ ጠቢቦች እድታከም አድርገሀል…በቃ አልተሳካም …እንደውም በአንተ ጥረት ነው የአንድ እና የሁለት አመት ቀሪ እድሜ ማግኘት የቻልኩት..ስለዚህ ይህቺን ባንተ ጥረት ያገኘኋትን ቀሪ ዕድሜዬን እንዳልከው በፍቅር እናጣጥምና ከዛ በሰላም ሸኘኝ …ባይሆን እዛ ጎጆ ቀይሼ መኖሪያ ቦታ አመቻችታ እጠብቅሀላሁ..››አለችና ጉንጩን በመሳም ስሩ ውሽቅ አለችበት..እሱም አጥብቆ አቀፋትና በአንድ እጁን ከአይኖቹ ሚንጠባጠበውን እንባ ማበስ ጀመረ ..
ከዚህ በላይ መቆየትም ሆነ በአላማዋ መግፋት አልቻለችም ….መኪናዋን አስነሳችና ወደቤቷ ነዳችው..ተቀጣጥሎ የነበረው የወሲብ ስሜቷ አሁን ከስሟል.‹‹.በዚህ አይነት ፍቅር ውስጥ እንዴት መግባት እችላለሁ?››..ይህቺንስ ሞት ፊት ለፊቷ የቆመባትን ሴት እንዴት መፎካከር ይቻላል… ?ከእሷ መንጠቅ ወይም መስረቅ በየትኛው ሞራል….?
እንደውም ከዚህ በላይ ታሪካቸውን ማወቅ ፈለገች..ልታግዛቸው ፡፡ከቻለች ለመሞከር….ግን ዛሬ አይደለም… ሌላ ቀን …በዚህን ሰዓት በዚህ የጨፈገገ ስሜቷ ውስጥ ሆና ምንም ማድረግ አልቻለችም..አሁን እቤቷ ገብታ ጥቅልል ብላ መተኛት ብቻ ነው የምትፈልገው…መኪናዋን እያከነፈች ነው… ንስሯ ክንፉን እያርገፈገፈ ጨለማውን በመሰንጠቅ ከፊቷ ይከንፋል..ሁኔታው የደስታ ነው….መጀመሪያም አካሄዷ ደስ አላሰኘውም ነበር….ሀሳቧን ቀይራ በቁዘማም ቢሆን ወደቤቷ መመለሷ እሱን እያስፈነጠዘው ነው…፡፡
""""
ምቾት የሌላው ምሽት ነበር ያሳለፈችው….ደግሞ ርዝመቱ እንደተለመደው 11 ሰዓት ከእንቅልፏ ተነሳችና እቤቷ ውሰጥ የተወሰነ የሰውነት እንቅስቃሴ ከሰራች በኃላ ወደበረንዳዋ ወጣች…ንሰሯ አብሯት ነበር የወጣው…..ለተወሰነ ደቂቃ ሀሳቧን ከራሷ ጋር ነበር ያደረገችው.. ኤርፎኗን ጆሮዋ ላይ ሰክታ ከሞባይሏ ለስለስ ያለ ሙዚቃ ከፍተችና እያዳመጠች ንጽህ የጥዋት አየር ወደ ሳንባዋ እየማገች ነው፡፡
ግን በመረጋጋት ውስጥ ሆና በጽሞና ሙዚቃውን ብቻ ማዳመጡን ቡዙም ልትዘልቀበት አልቻለችም..ሀሳቧ አሁንም ትናንት ላይ እንደተጣበቀ ነው…የብልቷ መብላት ቢተዋትም አዕምሮዋ ግን አሁንም ድረስ እያሳከከት ነው….እሷ እኮ ወንድ ልጅን ለዚህን ያህል ጊዜ ርዝመት በልቧ አዝላ አታውቅም… ፎክራ ስላላሳካችው ዝታ ስላልፈፀመች የመሸነፍ ቁጭት የፈጠረባት መብሰልሰል ይሆናል……….?
አዎ ከንስር ጋር እየኖሩ ሽንፈትን አሜን ብሎ በመቀበል አንገትን መድፋት የማይታሰብ ነው…በምክንያቱም ለንስር መታገል.. ታግሎም ማሸነፍ ተፈጥሮ ያደለው የብቻ ፀጋቸው ነው…ንስር የሞተ እንስሳ ንክች አያደርግም…የሚገድለውን ለማጥመድ ወይም ኢላማውን ለማግኘት መቶ ኪሎ ሜትር ሊያስስ ይችላል ..አስሶ አንዴ ራዳር ውስጥ ካስገባ ግን ንቅንቅ አይልም..ምንም ተአምር አያዘናጋውም…ግዳዩን ሳይጥል ውልፍች የለም…አዎ አድኖ አሳዶና ታግሎ በመጣል የገደለውን ብቻ ነው የሚበላው….፡፡እይታው ጠሊቅና እሩቅ ነው፡ካአለበት ቆሞ በአምስት ኪሎ ሜተር እርቀት ያለ ነገር ላይ ማነጣጠር ይችላል፡፡ልፋቱ የሌለበትን… አሸናፊነቱ የማይዘመርበትን ንክች አያደርግም… …ይህ የሰው ልጅም የህይወት መስመሩን ለማግኘት የተፈጠረበትን አለማ ለመገንዘብ የእድሜውን እሩብ ሊያባክን ይችላል…. ማባከኑም አግባብ ነው..መስመሩን ከያዘ በኃላ ግን አይኑም ቀልቡም መቶ ፐርሰንት መስመሩ ላይ መሆን አለበት፡፡ ትኩረቱም ጥረቱም ወደዛ ወደህይወት ግብ መዳረሻው የሚያደርሰው ሊሆን ይገባል…. የንስር ህይወት ይሄንን ነው የሚያስተምረው…
እሷም የሰለጠንችው በንስራ ስለሆነ ኢላማ ያደረገችበትን ነገር ከግብ ካላደረሰች ያማታል….አሁን እየተሰማት ያለው ስሜት ግን የተለየ ይመስላታል … ምክንያቱም ከባሪያው ልጅ ባልተናነሰ ቀዮ እጮኛውንም ከምናቧ ልታስወግዳት አልተቻለትም፡፡
‹‹አዎ መሞት የለባትም….በዚህ ዕድሜዋ መሞት አይገባትም››…ብላ በውስጧ ደመደመች…መልሳ ደግሞ እራሷን ሞገተች፡፡
‹‹ …በዚህ ዕድሜዋ መሞት የለባትም ስል ምን ማለቴ ነው..
…….?ሰው በስንት አመቱ ነው መሞት ያለበት……….?››ስትል አሰበች፡፡
ወጣት ሆኖ የሞተ ሰው ለምን በዛ ዕድሜዬ ሞትኩ ብሎ ይቆጫል ወይም ፈጣሪውን ይወቅሳል….? አይመስለኝም፡፡.ምን አልባት ይሄኛው አለም እና ከሞት ወዲያ ያለው ያኛው አለም ተብሎ ሚከፈል ዓለም ያለ ቢሆን እንኳን ያኛው አለም በእግዜር ሙሉ ቁጥጥር እና ፍቃድ የሚተዳደር ነው ሚሆነው..እንደዛ ከሆነ ደግሞ ከዚህኛው ዓለም ፍጽም የተሻለ ነው የሚሆነው..ያ ማለት ደግሞ ሞቶ ወደዛኛው አለም የተሸጋገረ ሰው በህፃንነቱም ሆነ በወጣትነቱ ቢሄድ ተገላገልኩ በምድር ከመሰቃየት፤ከመራብ፤ከመጠማት፤ከመጋዝና ከመታሰር እንኳንም በጊዜ ወደዚህ መጣሁ የሚል ይመስለኛል፡፡ሞት ማለት ሙሉ በሙሉ በስጋ መበስበስ እና በነፍስ መክሰም ወይም ወደ ምንምነትም መቀየር ከሆነ ደግሞ ለመፀፀት እና ለምን ቶሎ ሞትኩ …….?ብሎ ለማሰብም የሚያስችል ዕድልም አይኖርም ….ሞች በቋሚው አዕምሮ ሲመዘን ነው በልጅነቱ ተቀጨ..በወጣትነቱ ተቀጠፈ የሚባለው….እና አሁንም እሷ የልጅቷ እሞታለሁ ማለት ለምን ይሄን ያህል እንዳሳሰባት አልገባትም .. …….?ነው ወይስ ለተመኘችው ልጅ ስትል ይሆናል..…….?
‹‹እሱ እንዲያዝንብኝ ስላልፈለኩ ይሆን….?››ስትል እራሷን ትጠይቃለች ..ለጠየቀችው መልስ ከመፈለግ ይልቅ ግን ሌላ ጥያቄ እየጨመረችበት ነው….
እሷ እንደሆነ በመግደልም ሆነ በማዳን አታምንም…እንደእሷ እምነት ሰው የኖረበትን ጊዜ አጭርም ሆነ ረጅም ዋናው የኖረውን ያህል ተደስቶ መኖሩ ነው…..እርግጥ መግደል የእግዜያብሄር የአታድርግ ክልከላ ውስጥ ከሚካተቱ ትዕዛዞች መካከል አንዱ እንደሆነ ታውቃለች፡፡ቢሆንም ህይወት ከመግደልና ከመገደል ውጭ ህልውናዋ ፀንቶ እንደማይቆምም በተግባር አይታለች….ብዙ መግደል የቻለ ብዙ ይኖራል….ለመግደል የሰነፈ በጠንካራው ተገድሎ በሞቱ ለሌላው መኖር ምክንያት ሆኖ ያልፋል፡፡ይሄንን ከህይወት ተምራለች፡፡
ግን እግዚያብሄር አትግደል ሲል ለሰው ብቻ ነው እንዴ የሚሰራው..…….?ሰውን መግደል ብቻ ነው በኃጥያት የሚያስጠይቀው….? ለምን ….?ሰው በእግዜያብሄር ሀምሳል ስለተፈጠረ ልዩ መብት ስላለው….?፡፡ነው ወይስ ሰው የእግዜያብሄር ቤተ መቅደስ ነው የእግዜያብሄርን ቤተ መቅደስ ማፍረስ ደግሞ ያው ቀጥታ እሱን መዳፈር ነው…..ከእሱ ጋር መላተም ነው……ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ ተብሎ ስለሚታሰብ…..? …አትግደል የተባለው ነፍስ ያለውን ሁሉ ከሆነስ ……….?ያማ የማይቻል ከባድ ትዕዛዝ ይሆናል…፡፡ምክንያቱም እንስሳት ነፍስ አላቸው… ተክሎች ነፍስ አላቸው…ለመኖር ደግሞ ህይወት ያለው ነገር ሁሉ መመገብ አለበት..ለመመገብ ደግሞ አንዱ ዝርያ ሌላውን እየበላ ነው ነፍሱን የሚያቆየው…ለመብላት ደግሞ የግድ መግደል
👍93❤6👎6🔥2😁2
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹የትናንቶቹን ልጆች ሙሉ ታሪክ ማወቅ እፈለጋለሁ››ለንስሯ ነው እየነገረችው
‹‹ይቻላል››መለሰለት ዛፉ ላይ ሆኖ
‹‹በቃ አሁን ዝናቡ ሊዘንብ ነው …ዝናቡ ሲያባራ ታጣራልኛለህ››
በእሷ በማሾፍ በሚመስል ሁኔታ ክንፉን አርገፈገፈ…እሷ እንዲህ ያለችው ግቢዋ ውሰጥ ያሉ አዕዋፋት ዝናቡን ሽሽት በየዛፎቹ ቅርንጫፎች ሲሸሸጉ እና ወደጎጆቸው ሲገቡ ..ዝንጀሮዋችና ጉሬዛዎቾ ወደመጣለያቸው ሲሸጎጡ አይታ… እሷም ውሽንፍሩን በመፍራት ወደቤት ልትገባ መነሳቷን ከግምት በማስገባት ንስሯም እየዘነበ ካለው ዝናብ ለመጠለል አብሮኝ ተከትሎ ወደቤት ይገባል በሚል ግምት ነው…..በሀሳብ ውስጥ ሆና በዝንጉነት ያሰበችው ሀሳብ
ለካ ንስር ነው…
ንሰሯ አይኖ እያየ ወደላይ ተምዘገዘገ .እያነሰ እያነሰ ደመናውን ሰንጥቆ ከአይኗ ተሰወረ ….አዎ ከደመናው በላይ ብቻ ሳይሆን ከሚዘንበውም ዝናብም በላይ ነው የሆነው..እሷ ዝናብን ስትጠለል ንስሯ ንፍስ የቀላቀለውን ውሽንፍር እየሰነጠቀ በኩራትና በአሸናፊነት ከተዘረጋው ደመና እና ከሚረግፈው ዝናብ በላይ በመምጠቅ ቁልቁል እያየ ሊዝናናበት..
በንስሯ ሁኔታ ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ገባች…..ቁርስ ልታበስል አስባ ነበር …ግን ምንም አይነት የምግብ ፈልጎት ስለሌላት ወደመኝታ ክፍሏ ገባችና መልሳ አልጋዋ ላይ ወጣች..አዎ በዝናብ መኝታ ውስጥ ሆኖ ማሰብ ወይም ሙዚቃ ማዳመጥ የሚያስደስታት ነገር ነው…
‹‹እስቲ ንስሬ ስለትናንቱ ባሪያ ልጅ እና በቅርቡ ሟች ስለምትሆነው ፍቅረኛው ምን አይነት ታሪክ ይዞልኝ ይመጣ ይሆን ……….?የልጅቷስ የማይድነው በሽታዋስ ምን ይሆን….?እንድትሞት ልተዋት ..ወይስ ከንስሬ ጋር ሆኜ ላድናት……….?ቆይ እሱ እንደታሪካቸው ሁኔታ ነው የሚወሰነው….አሁን ንስሬ ከቅኝት ሲመለስ ልክ እንደተካታታይ የሆሊውድ ፊልም ታሪካቸውን ይዘረግፍልኛል….››
ምክንያቱን ባታውቅም ንስሯ ካሰበችው በላይ ቆየባት፡፡
ቆይ ቆይ እስኪ ድምጽ ይሰማኛል………….
ገርበብ ያለው መኝታ ቤት ተበረግዶ ተከፈተ…ሌላ ሰው አይደለም ንስሯ ነው….በራፉን በመንቁሩ ስቦ በመበርገድ በሮ አልጋዋ ላይ ከጎኗ ጉብ ያለው… ክንፎቹን ወደ ውስጥ ሰብስቦ አንገቱን ቀብሮ ሽብልል ብሎ ተኛ…ጥሩ ነገር ይዞላት እንዳልመጣ ገባት…ሁልጊዜ የሆነ ነገር እንዲያጣራላት ልካው ያገኘው መረጃ አና ከምፈልገው በተቃራኒ ከሆነ እንዲህ ነው ዝልፍልፍ የሚለው…ዝልፍልፍ ማለት ደግሞ በእሱ አያምርም፡፡
የንስሯን ሁኔታ ሰለልጁ ታሪክ ለማወቅ ያለቻትን ጉጉት በእጥፍ ጨመረበት..እራሷን አስተካክላ ሀሳቧን ሰብስባ ወደንስሯ አዕምሮ ዘልቃ ገባች..ያየውን ለማየት…ያወቀውን ለማወቅ
//
የትናንትናው ቀልቧን ሰልቧት የነበረው ባሪያው ልጅ መላኩ ይባላል ..እሷ ማለት ከሞት ጋር ቀጠሮ ይዛ በስጋት ኑሮ ላይ ያለችው ፍቅረኛው ስም ደግሞ ሰሚራ ትባላለች…ሁለቱ የተገናኙት ከአራት አመት በፊት ነው….
ንስሯም ስለሁለቱ ፍቅረኛሞች ይዞላት የመጣው ታሪክ መነሻው ከተገናኙበት የዛሬ አራት አመት ወዲህ ያለውን ነው……
አዎ ሰሚራ ነርስ ነች …በአንድ የግል ሆስፒታል ውስጥ በነርስነት በምትሰራበት እና ተረኛ ሆና የስራ ገበታው ላይ በነበረችበት በአንድ ቀን ከ4 ዓመት በፊት ማለት ነው፡፡አንድ ወጣት በሞት እና በህይወት መካከል ተንጠልጥሎ አረፋ ደፍቆ እያቃተተ በአንብላንስ ተጭኖ ይመጣል..
አጋጣሚ ሆኖ በዕለቱ ሰሚራ ተረኛ እንደመሆኗ መጠን ከሌሎች ዶክተሮች ጋር ሆና የመጣውን በሽታኛ ህይወት ለማትረፍ ባለአቅማቸው እና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም ይሯሯጣሉ…. ወጣቱ ኃይለኛ ገዳይ መርዝ በመላ ሰውነቱን ተሰራጭቶ አንጀቱን እየበጣጠሰው ነበር ....ከዛ በእነሱ ጥረት የእግዜርም በጎ ፍቃድ ተጨምሮበት ከመሞት ይተራፋል… ግን ጉዳቱ ከፍተኛ ስለነበር ከገባበት ኮማ ለመንቃት አልቻለም ነበር….ስለሆነም የጤናው ሁኔታ በአስተማማኝ ሁኔታ እስኪስተካከል እዛው ሆስፒታል ተኝቶ ክትትል እንዲያደርግ ይወሰናል…
ያ ወጣት ሆስፒታል ከገባበት ቀን አንስቶ አብረውት የነበሩ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ ጎልማሶች ነበሩ….ሰሚራ በወቅቱ ከእነሱ ከራሳቸው ጠይቃ እንደተረዳችው ሴቷ የበሽተኛው ፍቅረኛ ወንዱ ደግሞ በአባት የሚገናኘው ግማሽ ወንድሙ …..….በተጨማሪም ፖሊሶችም ገባ ወጣ ይሉ ነበር…የበሽተኛውን መንቃት ተከትሎ የሚሰጠውን ቃል ለመቀበል…
እሷም ምንም እንኳን የስራዋ አንዱ ግዳጅ እና ኃላፊቷ ቢሆንም ግን በማታውቀው ሌላ ተጨማሪ የተለየ ስሜት እየተገፋፋች በከፍተኛ ሁኔታ ስትንከባከበው ትቆያለች…አብረውት የሚያሰትምሙት ቤተሰቦቹ እስኪገረሙባት ድረስ፡፡በሽተኛው እስከ ሶስተኛው ቀን ድረስ ከገባበት ኮማ መንቃት አልቻለም ነበር ፤በአራተኛው ቀን ግን ለ5 ደቂቃ ያህል አይኖቹን መግለጥ እና አንደበቱን ማላቀቅ ቻለ..የመዳን ተስፋው በእጥፍ ጨመረ፤ይሄ ሁኔታ ሰሚራን እና ጓደኞቾን በጣም ቢያስደስታቸውም የመላኩን አሰታማሚ ቤተሰቦች ግን በሚገርም ሁኔታ አለመረጋጋት እና ድንጋጤ ውስጥ ከተታቸው፤ይህንንም ጉዳይ ሰሚራ መታዘብ ስለቻለች ግራ ተጋብታ ትዝብቷን በውስጧ ቀብራ ስትብሰለሰል ትሰነብታለች፤በአምስተኛው ቀን ግን ሰሚራ የእለት ስራዋን አጠናቃ ወደቤቷ ስትመለስ የመላኩ አስታማሚዎች እቤቷ በራፍ ላይ ቆመው ሲጠብቋት አገኘች
ሰሚራም ደንግጣ‹‹ምን ተፈጠረ..….?ምን እግር ጣላችሁ….?››
ሰላም ምትባለው…የመላኩ እጮኛ‹‹ተረጋጊ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነው….?››አለቻት፡፡
‹‹ምንድነው ምታማክሩኝ …….?ደግሞስ ሆስፒታል ተገናኝተን አልነበር..እዛው እኮ ልትጠይቁኝ ትችሉ ነበር…?››
የበሽተኛው ግማሽ ወንድም የሆነው ሰሎሞን‹‹አይ እዛማ በስራ ወከባ ላይ ስለሆንሽ የግል ጉዳይ ለማውራት አይመችም ብለን ነው››
ግራ ትጋባና ‹‹የግል ጉዳይ …….?ማለት ስለ መላኩ ጤንነት ማለታችሁ ነው….?›› ብላ ጠየቀች…ሌላ ከእሷ ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ አልታይሽ ብሏት፡፡
ሰላም እያቅማማች ‹‹አዎ ግን ካላስቸገርንሽ ወይ እቤትሽ ገብተን ወይ ደግሞ ሌላ ቦታ ሄደን ብናናግርሽ››
ሰሚራ ምታደርገውም ምትናገረውም ግራ ገብቷት ወደ ቤቷ ይዛቸው ትገባለች…ወደቤት ከገቡ በኃላ ለውይይት ያቀረቡላት ርዕስ ከጠበቀችው በጣም የራቀና አስደንጋጭ ነበር…››
የግማሽ ሚሊዬን ብር ቼክ በእጇ ላይ ካስቀመጡላት በኃላ ….‹‹መላኩን እንዳይድን አድርጊልን››ነበር ያሏት፡፡
‹‹እንዴ ለምን…….?ለአንቺ ፍቅረኛሽ ለአንተ ደግሞ ወንድምህ አይደል…….?ነው ወይስ ዋሽታችሁኛል….?፡፡››
‹‹አይ እሱን አልዋሸንሽም…ግን አንቺ ማይገባሽ ብዙ ጉዳዬች አሉ..አሁን ብታድኝው እራሱ ሙሉ ጤነኛ አይሆንም ..አካሉ እንደልብ ላይታዘዝለት ይችላል..ወይም አዕምሮው የማሰብ አቅሙ ተዛብቶ ዘገምተኛ ሆኖ ሊቀር ይችላል….እንደዛ የመሆን እድል እንደሚገጥመው ደግሞ የነገራችሁን እናንተው ናችሁ፡፡››
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹የትናንቶቹን ልጆች ሙሉ ታሪክ ማወቅ እፈለጋለሁ››ለንስሯ ነው እየነገረችው
‹‹ይቻላል››መለሰለት ዛፉ ላይ ሆኖ
‹‹በቃ አሁን ዝናቡ ሊዘንብ ነው …ዝናቡ ሲያባራ ታጣራልኛለህ››
በእሷ በማሾፍ በሚመስል ሁኔታ ክንፉን አርገፈገፈ…እሷ እንዲህ ያለችው ግቢዋ ውሰጥ ያሉ አዕዋፋት ዝናቡን ሽሽት በየዛፎቹ ቅርንጫፎች ሲሸሸጉ እና ወደጎጆቸው ሲገቡ ..ዝንጀሮዋችና ጉሬዛዎቾ ወደመጣለያቸው ሲሸጎጡ አይታ… እሷም ውሽንፍሩን በመፍራት ወደቤት ልትገባ መነሳቷን ከግምት በማስገባት ንስሯም እየዘነበ ካለው ዝናብ ለመጠለል አብሮኝ ተከትሎ ወደቤት ይገባል በሚል ግምት ነው…..በሀሳብ ውስጥ ሆና በዝንጉነት ያሰበችው ሀሳብ
ለካ ንስር ነው…
ንሰሯ አይኖ እያየ ወደላይ ተምዘገዘገ .እያነሰ እያነሰ ደመናውን ሰንጥቆ ከአይኗ ተሰወረ ….አዎ ከደመናው በላይ ብቻ ሳይሆን ከሚዘንበውም ዝናብም በላይ ነው የሆነው..እሷ ዝናብን ስትጠለል ንስሯ ንፍስ የቀላቀለውን ውሽንፍር እየሰነጠቀ በኩራትና በአሸናፊነት ከተዘረጋው ደመና እና ከሚረግፈው ዝናብ በላይ በመምጠቅ ቁልቁል እያየ ሊዝናናበት..
በንስሯ ሁኔታ ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ገባች…..ቁርስ ልታበስል አስባ ነበር …ግን ምንም አይነት የምግብ ፈልጎት ስለሌላት ወደመኝታ ክፍሏ ገባችና መልሳ አልጋዋ ላይ ወጣች..አዎ በዝናብ መኝታ ውስጥ ሆኖ ማሰብ ወይም ሙዚቃ ማዳመጥ የሚያስደስታት ነገር ነው…
‹‹እስቲ ንስሬ ስለትናንቱ ባሪያ ልጅ እና በቅርቡ ሟች ስለምትሆነው ፍቅረኛው ምን አይነት ታሪክ ይዞልኝ ይመጣ ይሆን ……….?የልጅቷስ የማይድነው በሽታዋስ ምን ይሆን….?እንድትሞት ልተዋት ..ወይስ ከንስሬ ጋር ሆኜ ላድናት……….?ቆይ እሱ እንደታሪካቸው ሁኔታ ነው የሚወሰነው….አሁን ንስሬ ከቅኝት ሲመለስ ልክ እንደተካታታይ የሆሊውድ ፊልም ታሪካቸውን ይዘረግፍልኛል….››
ምክንያቱን ባታውቅም ንስሯ ካሰበችው በላይ ቆየባት፡፡
ቆይ ቆይ እስኪ ድምጽ ይሰማኛል………….
ገርበብ ያለው መኝታ ቤት ተበረግዶ ተከፈተ…ሌላ ሰው አይደለም ንስሯ ነው….በራፉን በመንቁሩ ስቦ በመበርገድ በሮ አልጋዋ ላይ ከጎኗ ጉብ ያለው… ክንፎቹን ወደ ውስጥ ሰብስቦ አንገቱን ቀብሮ ሽብልል ብሎ ተኛ…ጥሩ ነገር ይዞላት እንዳልመጣ ገባት…ሁልጊዜ የሆነ ነገር እንዲያጣራላት ልካው ያገኘው መረጃ አና ከምፈልገው በተቃራኒ ከሆነ እንዲህ ነው ዝልፍልፍ የሚለው…ዝልፍልፍ ማለት ደግሞ በእሱ አያምርም፡፡
የንስሯን ሁኔታ ሰለልጁ ታሪክ ለማወቅ ያለቻትን ጉጉት በእጥፍ ጨመረበት..እራሷን አስተካክላ ሀሳቧን ሰብስባ ወደንስሯ አዕምሮ ዘልቃ ገባች..ያየውን ለማየት…ያወቀውን ለማወቅ
//
የትናንትናው ቀልቧን ሰልቧት የነበረው ባሪያው ልጅ መላኩ ይባላል ..እሷ ማለት ከሞት ጋር ቀጠሮ ይዛ በስጋት ኑሮ ላይ ያለችው ፍቅረኛው ስም ደግሞ ሰሚራ ትባላለች…ሁለቱ የተገናኙት ከአራት አመት በፊት ነው….
ንስሯም ስለሁለቱ ፍቅረኛሞች ይዞላት የመጣው ታሪክ መነሻው ከተገናኙበት የዛሬ አራት አመት ወዲህ ያለውን ነው……
አዎ ሰሚራ ነርስ ነች …በአንድ የግል ሆስፒታል ውስጥ በነርስነት በምትሰራበት እና ተረኛ ሆና የስራ ገበታው ላይ በነበረችበት በአንድ ቀን ከ4 ዓመት በፊት ማለት ነው፡፡አንድ ወጣት በሞት እና በህይወት መካከል ተንጠልጥሎ አረፋ ደፍቆ እያቃተተ በአንብላንስ ተጭኖ ይመጣል..
አጋጣሚ ሆኖ በዕለቱ ሰሚራ ተረኛ እንደመሆኗ መጠን ከሌሎች ዶክተሮች ጋር ሆና የመጣውን በሽታኛ ህይወት ለማትረፍ ባለአቅማቸው እና ቴክኖሎጂውን በመጠቀም ይሯሯጣሉ…. ወጣቱ ኃይለኛ ገዳይ መርዝ በመላ ሰውነቱን ተሰራጭቶ አንጀቱን እየበጣጠሰው ነበር ....ከዛ በእነሱ ጥረት የእግዜርም በጎ ፍቃድ ተጨምሮበት ከመሞት ይተራፋል… ግን ጉዳቱ ከፍተኛ ስለነበር ከገባበት ኮማ ለመንቃት አልቻለም ነበር….ስለሆነም የጤናው ሁኔታ በአስተማማኝ ሁኔታ እስኪስተካከል እዛው ሆስፒታል ተኝቶ ክትትል እንዲያደርግ ይወሰናል…
ያ ወጣት ሆስፒታል ከገባበት ቀን አንስቶ አብረውት የነበሩ አንድ ሴት እና አንድ ወንድ ጎልማሶች ነበሩ….ሰሚራ በወቅቱ ከእነሱ ከራሳቸው ጠይቃ እንደተረዳችው ሴቷ የበሽተኛው ፍቅረኛ ወንዱ ደግሞ በአባት የሚገናኘው ግማሽ ወንድሙ …..….በተጨማሪም ፖሊሶችም ገባ ወጣ ይሉ ነበር…የበሽተኛውን መንቃት ተከትሎ የሚሰጠውን ቃል ለመቀበል…
እሷም ምንም እንኳን የስራዋ አንዱ ግዳጅ እና ኃላፊቷ ቢሆንም ግን በማታውቀው ሌላ ተጨማሪ የተለየ ስሜት እየተገፋፋች በከፍተኛ ሁኔታ ስትንከባከበው ትቆያለች…አብረውት የሚያሰትምሙት ቤተሰቦቹ እስኪገረሙባት ድረስ፡፡በሽተኛው እስከ ሶስተኛው ቀን ድረስ ከገባበት ኮማ መንቃት አልቻለም ነበር ፤በአራተኛው ቀን ግን ለ5 ደቂቃ ያህል አይኖቹን መግለጥ እና አንደበቱን ማላቀቅ ቻለ..የመዳን ተስፋው በእጥፍ ጨመረ፤ይሄ ሁኔታ ሰሚራን እና ጓደኞቾን በጣም ቢያስደስታቸውም የመላኩን አሰታማሚ ቤተሰቦች ግን በሚገርም ሁኔታ አለመረጋጋት እና ድንጋጤ ውስጥ ከተታቸው፤ይህንንም ጉዳይ ሰሚራ መታዘብ ስለቻለች ግራ ተጋብታ ትዝብቷን በውስጧ ቀብራ ስትብሰለሰል ትሰነብታለች፤በአምስተኛው ቀን ግን ሰሚራ የእለት ስራዋን አጠናቃ ወደቤቷ ስትመለስ የመላኩ አስታማሚዎች እቤቷ በራፍ ላይ ቆመው ሲጠብቋት አገኘች
ሰሚራም ደንግጣ‹‹ምን ተፈጠረ..….?ምን እግር ጣላችሁ….?››
ሰላም ምትባለው…የመላኩ እጮኛ‹‹ተረጋጊ አንድ ነገር ልናማክርሽ ነው….?››አለቻት፡፡
‹‹ምንድነው ምታማክሩኝ …….?ደግሞስ ሆስፒታል ተገናኝተን አልነበር..እዛው እኮ ልትጠይቁኝ ትችሉ ነበር…?››
የበሽተኛው ግማሽ ወንድም የሆነው ሰሎሞን‹‹አይ እዛማ በስራ ወከባ ላይ ስለሆንሽ የግል ጉዳይ ለማውራት አይመችም ብለን ነው››
ግራ ትጋባና ‹‹የግል ጉዳይ …….?ማለት ስለ መላኩ ጤንነት ማለታችሁ ነው….?›› ብላ ጠየቀች…ሌላ ከእሷ ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ አልታይሽ ብሏት፡፡
ሰላም እያቅማማች ‹‹አዎ ግን ካላስቸገርንሽ ወይ እቤትሽ ገብተን ወይ ደግሞ ሌላ ቦታ ሄደን ብናናግርሽ››
ሰሚራ ምታደርገውም ምትናገረውም ግራ ገብቷት ወደ ቤቷ ይዛቸው ትገባለች…ወደቤት ከገቡ በኃላ ለውይይት ያቀረቡላት ርዕስ ከጠበቀችው በጣም የራቀና አስደንጋጭ ነበር…››
የግማሽ ሚሊዬን ብር ቼክ በእጇ ላይ ካስቀመጡላት በኃላ ….‹‹መላኩን እንዳይድን አድርጊልን››ነበር ያሏት፡፡
‹‹እንዴ ለምን…….?ለአንቺ ፍቅረኛሽ ለአንተ ደግሞ ወንድምህ አይደል…….?ነው ወይስ ዋሽታችሁኛል….?፡፡››
‹‹አይ እሱን አልዋሸንሽም…ግን አንቺ ማይገባሽ ብዙ ጉዳዬች አሉ..አሁን ብታድኝው እራሱ ሙሉ ጤነኛ አይሆንም ..አካሉ እንደልብ ላይታዘዝለት ይችላል..ወይም አዕምሮው የማሰብ አቅሙ ተዛብቶ ዘገምተኛ ሆኖ ሊቀር ይችላል….እንደዛ የመሆን እድል እንደሚገጥመው ደግሞ የነገራችሁን እናንተው ናችሁ፡፡››
👍70😱8❤4🥰1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ለሊቱ ያለእንቅልፍ ነው ያለፈው….የጣር ለሊት…የስቃይ ለሊት…፡፡ደግነቱ ፕሮፌሰሩ ለሊቱን ሙሉ አብረዋት ነው ያሳለፍት…..ይሁን እንጂ እሷ ባዘነች መጠን አብረዋት እያዘኑ ነበር ብሎ በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም..ግን በታታሪት ሲያዳምጧት እና ደረቅ አልኳል ሲያጣጧት ነበር.. ወፎች የለሊቱን መንጋት የምስራች ሊያበስሩ ሲንጫጩ ድምጻቸው የተሰማው…
ሁለት ጠርሙስ ብላክ ሌብል ጠርሙስ ጨርሰዋል..እሷ አንድ ጠርሙስ ከግማሹን ሳትጨርስ አልቀርም፡፡በንዴት፤ በስጋትና በብስጭት ያወራችው ወሬ ቢቀረብ እና ወደ መጻሀፍ ቢገለበጥ አንድ ደለብ ያለ መጽሀፍ ይወጣዋል፡፡
‹‹ፕሮፌሰር ምን አቀበጠኝና ተክሉን ቀነጠስኩ..….?ምን ቅብጥ አደረገኝ….?››
‹‹እንደነገርሺኝ እኮ ሙሉ በሙሉ ሚያመጣውን መዘዝ አልተረዳሽም ነበር››
‹‹እኮ ረጋ ብዬ ጊዜ ወስጄ ማሰብ ነበረብኝ…ንስሬ እንኳን ሊነግረኝ ባይፈልግ…ጎትጉቼ ሙሉውን መዘዝ መረዳት ነበረብኝ፡፡››
‹‹ግን እርግጠኛ ነሽ ..እንደዚህ ያለ ንስርሽ ለመሄድ እንደምትገደጂ ብታውቂ ኖሮ ተክሏን ከመቀንጠስ ትታቀቢ ነበር….?››
‹‹ይቀልዳሉ እንዴ ፕሮፌሰር..ጭርሽ ለማሰብ እንኳን አልሞክርም…እንዴ ንስሬን ጥዬ እንኳን የማላውቃቸው ..ምን አይነት ፍጡር እንደሆኑ እንኳን እርግጠኛ ወዳልሆንኩባቸው..ይመቹኝ አይመቹኝ መገመት ወደማልችላቸው የአባቴ ዘመዶች ይቅርና እግዚያብሄርም ቢጠራኝ ንስሬን ጥዬ በፍቃደኝነት ለመሄድ አልፈልግም››
‹‹በቃ ተረጋጊ..ያው በሞትም መለየት እኮ አለ››አሏት ፕሮፈሰሩ …በእሳቸው ቤት እሷን የሚያጽናና ቃል መናገራቸው ነው፡፡
‹‹አይ ፕሮፌሰር …ይቀልዱብኛል አይደል?ይሄም እኮ ያው ሞት ነው…ሞት ማለት የራስ ከሆኑ ሰዎችና ከሚኖሩበት ዓለም ለዘላለም ተለይቶ በስጋ ወደመሬት ውስጥ መግባት በነፍስ ደግሞ ወደማይታወቅ አለም መጓዝ ማለት አይደል…?አሁን እኔም ከሳምንት በኃላ የሚገጥመኝ ደግሞ በስጋም በነፍስም ከዚህች ምድርም ሆነ የእኔ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ ተለይቼ ለዘላለም ወደማይታወቅ አለም በስጋም በነፍስም መጓዝ ነው…ታዲያ ይሄ እንደውም ሙሉ ሞት አይደለም..….?ማንም ሰው ስናፍቀው እንኳን መቃብሬ ጋር ሄዶ በማልቀስ ወይም አበባ በማኖር ሊያጽናና ዕድሉ አይኖረውም …. ነፍሴንም ስጋዬንም ይዤ ነው የምሄደው…››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው››
‹‹አዎ ዋናው ችግር ግን ይሄ አይደለም..ዋናው ንስሬን ጥዬ መሄድ ያለመፈለጌ ነው..እሱን..››ንግግሯን አቋረጧት፡፡
‹‹እኔ እኮ በህይወት እስካለሁ ድረስ ልንከባከብልሽ እችላለሁ፡፡››
‹‹አይ አይችሉም… እርሶ የሚችሉት በስርዓት የቀብር ሰርዓቱን ማስፈፀም ብቻ ነው››
‹‹አልገባኝም..››አሏት ደንግጠው፡፡
‹‹እኔ ጥዬው በሄድኩ ቀን እሱም እደሚሞት ነግሮኛል››
‹‹እንዴት ሆኖ ነው የሚሞተው….?››
‹‹እኔ እንጃ ግን እኔን ከወሰዱኝ በኃላ ለአንድ ቀንም እንኳን በህይወት መኖር እንደማይችል እርግጠኛ ሆኖ ነግሮኛል››
‹‹አይዞሽ ሳምንት እኮ ብዙ ቀን ነው..የሆነ መውጫ መንገድ ልናገኝ እንችላለን..በተለይ ንስርሽ መላ ሚያጣ አይመስለኝም››
‹‹እኔ እንጃ …. እንደዛ ተስፋ አላደርግም …››
‹‹አይዞሽ…ደግሞ ይሄ ጉዳይን እንደመስዋዕትነት ቁጠሪው..ህይወት ለማትረፍ ነው እዚህ ወጥመድ ውስጥ የገባሽው››
‹‹መስዋዕት አሉኝ….መስዋዕትነትማ እንዲህ በቀልድ አይገለጽም..እኔ ከመስዋዕትነት ይልቅ ክስረት ነው የሚሰማኝ…መስዋዕትነት እኮ ለአንድ ክብር አለማ አቅዶና አስቦ ሕይወትንም ጭምር መስጠት ማለት ነው…ህይወትንም ጭምር ቢሆን አጥቶ ሌላውን ለማኖር ቀድሞም አምኖና ወስኖ መተግበር ማለት ነው…
‹‹ልክ እንደ አርበኞቻችን ማለትሽ ነው….?››
‹‹አዎ እንደውም ዛሬ ለሀገር መስዋዕትነት ስለከፈሉ ሰዎች ምስጋና የምናቀርብበት ቀን አይደል…ሀገር ከምትደፈር የእኔ ህይወት ትቀጠፍ ብለው…ለልጆችና ለልጅ ልጆቻችን ባርነትን ከምናወርስ እኛ ዛሬ ደማችንን እረጭተን አጥንታችንን በትነን ነጻነትና ኩራትን እናወርሳቸው ብለው ታሪክ እንደሰሩት አባቶቻችን ነው መስዋዕትነት….ልክ እንደ በላይ ዘለቀ፡፡ ከገዛ አብራክ ልጅ ይልቅ ሀገርን ወይም ህዝብን ማስቀደም ማለት ነው…ለሀገር ክብር እና ለወገን መድህን ሆኖ መውደቅ ማለት ነው…ከስኬት በኃላም ላደረጉት ነገር የተለየ ክብር እና ሹመት አለመፈለግ ማለት ነው..ለሚወዱት ነገር ያለንን ነገር ሁሉ ህይወትንም ጭምር በነፃ መስጠት ማለት ነው….
እንደዛአይነት መስዋዕትነት ሚስጥሩ ከባድ ነው….ከድል በኃላ የበላይን ይሄንን ለሀገሩ በነፃ የሰጠውን መስዋዕትነት ሸፍጠኞቹ እና ባንዳዎቹ አልወደዱለትም ነበር..ምክንያም ስለእሱ ዝናና ታሪክ ሲሰሙ የእነሱን ሆዳምነት እና ትንሽነታቸውን በየጊዜው ስለሚያሳብቅባቸው ከንጉሱ አላትመው በአደባባይ እንዲሰቀል አደረጉት..ከጠላት በክብር የተረፈች ነፍሱ በገዛ ህዝቦቹ ምቀኝነት እና ክፍት ተነጠቀች…ይሄ ነው መስዋዕትነትን መራር የሚያደርገው…ለዚህ ነው መስዋዕትነት የሚለው ቃል ሚያስጠላኝ፡፡
‹‹ትክክል ነሽ ልጄ…ይሄ የበላይ ታሪክ የእንግሊዞች ቢሆን፤ይሄ የበላይ ታሪክ የአሜሪካኖች ቢሆን ኖሮ አንድ ሺ ፊልም እና አስር ሺ መጽሀፍ ተጽፎበት ነበር…?ስንት መንገድ እና ስንት ዩኒቨርሲቲ በስሙ ተሰይሞለት ነበር…?››
እኚህ ለሊቱን ከፕሮፌሰሩ ጋር በመጠጥ እያወራረድ በእሷ ለቅሷ ታጅበው ሲያወሩ ከነበሩት ነጥቦች ጥቂቶቹ ነበሩ..….
አሁን ሰዕቱ ከማለዳ 12፡45 ይላል…ፕሮፈሰሩ በመጠጥ እና በእሷ ወሬ ተዳክመው ይመስላል እዛው የተቀመጡበት ሶፋ ላይ ደገፍ እንደሉ እንቅልፍ ይዞቸው ጭልጥ ብሏል….ንስሯ ያለው መኝታ ቤት ውሰጥ ነው ከእሷ በላይ ትካዜና ቁዘማ ውስጥ ነው…ልትነካካው አልፈለገችም
እየተንገዳገደች እቤቱን ለቃ ወጣችና ወደ መኪና ማቆሚያ አመራች…‹‹ከጠጡ አይንዱ›› የሚለውን የትራፊኮችን ዋና ምክር አዘል መመሪያ ከቁብም ሳትቆጥር መኪናዋን አስነሳችና ግቢው ለቃ ተፈተለከች..ቀጥታ ወደመላኩ ቤት ነው ያመራችው…
እንደደረሰች ወደጊቢው አጥር አስጠጋችና መንገድ እንዳይዘጋ አስተካክላ መኪናዋን ካቆመች በኃላ ሞተሩን በማጥፋት ከመኪናዋ ወረደችና የግቢውን በራፍ መጥሪያ በሰከንድ ሽርፋራፊ ውስጥ ደጋግማ አንጣረረችው ፡፡ከጠበቀችው በፈጠነ ሁኔታ ተከፈተላተት..ከእንቅልፉ የባነነ እና በአንድ እጁ አይኖቹን እያሻሸ በሌላ እጁ የበራፍን እጄታ ይዞ ‹‹ምን ፈለግሽ….? ›› የሚላት ሰው ስትጠብቅ .. ንቁ እንቅልፍ በዓይኑ እንዳልዞረ የሚያስታውቅ..አይ እንደውም እያለቀሰ የነበረ ከዚህ በፊትም ያየችት ዘበኛ ከፈተላትና…ምንም ነገር ሳይጠይቃት እንድትገባ መንገዱን ዞር ብሎ ለቀቀለት …አልፋ ገባችና መንገዷን ቀጠለች ..በፍጥነት ዘግቷ ከኃላዋ ተከተላት፡፡
‹‹ዛሬ ምን አይነት ቀን ነው…….?ሰው ሁሉ ሲያለቅስ እንቅልፍ አጥቶ የሚያድርበት ቀን ነው እንዴ….?››ከዘበኛው ሁኔታ ተነስታ ውስጧን እየጠየቀች ነው… እራሷን ለመቆጣጠር በዚህ በተወለካከፈ እርምጃ አንድ ነገር አደናቅፏኝ እንዳትደፋ እየፈራች ስትራመድ ዘበኛው በታፈነ ድምጽ መናገር ጀመረ
‹‹ጋሼ ደውለውልሽ ነው….?››
‹‹አዎ›› አለችው….ምንም ሳታስብበት
‹‹አይ ቢጨንቃቸው እኮ ነው ..በቃ እኮ 10 ደቂቃም ዕድሜ አይራቸውም …አብቅቶላቸዋል…››
‹‹ማን ነው ያበቃለት ….?››ደንግጣ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ለሊቱ ያለእንቅልፍ ነው ያለፈው….የጣር ለሊት…የስቃይ ለሊት…፡፡ደግነቱ ፕሮፌሰሩ ለሊቱን ሙሉ አብረዋት ነው ያሳለፍት…..ይሁን እንጂ እሷ ባዘነች መጠን አብረዋት እያዘኑ ነበር ብሎ በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም..ግን በታታሪት ሲያዳምጧት እና ደረቅ አልኳል ሲያጣጧት ነበር.. ወፎች የለሊቱን መንጋት የምስራች ሊያበስሩ ሲንጫጩ ድምጻቸው የተሰማው…
ሁለት ጠርሙስ ብላክ ሌብል ጠርሙስ ጨርሰዋል..እሷ አንድ ጠርሙስ ከግማሹን ሳትጨርስ አልቀርም፡፡በንዴት፤ በስጋትና በብስጭት ያወራችው ወሬ ቢቀረብ እና ወደ መጻሀፍ ቢገለበጥ አንድ ደለብ ያለ መጽሀፍ ይወጣዋል፡፡
‹‹ፕሮፌሰር ምን አቀበጠኝና ተክሉን ቀነጠስኩ..….?ምን ቅብጥ አደረገኝ….?››
‹‹እንደነገርሺኝ እኮ ሙሉ በሙሉ ሚያመጣውን መዘዝ አልተረዳሽም ነበር››
‹‹እኮ ረጋ ብዬ ጊዜ ወስጄ ማሰብ ነበረብኝ…ንስሬ እንኳን ሊነግረኝ ባይፈልግ…ጎትጉቼ ሙሉውን መዘዝ መረዳት ነበረብኝ፡፡››
‹‹ግን እርግጠኛ ነሽ ..እንደዚህ ያለ ንስርሽ ለመሄድ እንደምትገደጂ ብታውቂ ኖሮ ተክሏን ከመቀንጠስ ትታቀቢ ነበር….?››
‹‹ይቀልዳሉ እንዴ ፕሮፌሰር..ጭርሽ ለማሰብ እንኳን አልሞክርም…እንዴ ንስሬን ጥዬ እንኳን የማላውቃቸው ..ምን አይነት ፍጡር እንደሆኑ እንኳን እርግጠኛ ወዳልሆንኩባቸው..ይመቹኝ አይመቹኝ መገመት ወደማልችላቸው የአባቴ ዘመዶች ይቅርና እግዚያብሄርም ቢጠራኝ ንስሬን ጥዬ በፍቃደኝነት ለመሄድ አልፈልግም››
‹‹በቃ ተረጋጊ..ያው በሞትም መለየት እኮ አለ››አሏት ፕሮፈሰሩ …በእሳቸው ቤት እሷን የሚያጽናና ቃል መናገራቸው ነው፡፡
‹‹አይ ፕሮፌሰር …ይቀልዱብኛል አይደል?ይሄም እኮ ያው ሞት ነው…ሞት ማለት የራስ ከሆኑ ሰዎችና ከሚኖሩበት ዓለም ለዘላለም ተለይቶ በስጋ ወደመሬት ውስጥ መግባት በነፍስ ደግሞ ወደማይታወቅ አለም መጓዝ ማለት አይደል…?አሁን እኔም ከሳምንት በኃላ የሚገጥመኝ ደግሞ በስጋም በነፍስም ከዚህች ምድርም ሆነ የእኔ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ ተለይቼ ለዘላለም ወደማይታወቅ አለም በስጋም በነፍስም መጓዝ ነው…ታዲያ ይሄ እንደውም ሙሉ ሞት አይደለም..….?ማንም ሰው ስናፍቀው እንኳን መቃብሬ ጋር ሄዶ በማልቀስ ወይም አበባ በማኖር ሊያጽናና ዕድሉ አይኖረውም …. ነፍሴንም ስጋዬንም ይዤ ነው የምሄደው…››
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው››
‹‹አዎ ዋናው ችግር ግን ይሄ አይደለም..ዋናው ንስሬን ጥዬ መሄድ ያለመፈለጌ ነው..እሱን..››ንግግሯን አቋረጧት፡፡
‹‹እኔ እኮ በህይወት እስካለሁ ድረስ ልንከባከብልሽ እችላለሁ፡፡››
‹‹አይ አይችሉም… እርሶ የሚችሉት በስርዓት የቀብር ሰርዓቱን ማስፈፀም ብቻ ነው››
‹‹አልገባኝም..››አሏት ደንግጠው፡፡
‹‹እኔ ጥዬው በሄድኩ ቀን እሱም እደሚሞት ነግሮኛል››
‹‹እንዴት ሆኖ ነው የሚሞተው….?››
‹‹እኔ እንጃ ግን እኔን ከወሰዱኝ በኃላ ለአንድ ቀንም እንኳን በህይወት መኖር እንደማይችል እርግጠኛ ሆኖ ነግሮኛል››
‹‹አይዞሽ ሳምንት እኮ ብዙ ቀን ነው..የሆነ መውጫ መንገድ ልናገኝ እንችላለን..በተለይ ንስርሽ መላ ሚያጣ አይመስለኝም››
‹‹እኔ እንጃ …. እንደዛ ተስፋ አላደርግም …››
‹‹አይዞሽ…ደግሞ ይሄ ጉዳይን እንደመስዋዕትነት ቁጠሪው..ህይወት ለማትረፍ ነው እዚህ ወጥመድ ውስጥ የገባሽው››
‹‹መስዋዕት አሉኝ….መስዋዕትነትማ እንዲህ በቀልድ አይገለጽም..እኔ ከመስዋዕትነት ይልቅ ክስረት ነው የሚሰማኝ…መስዋዕትነት እኮ ለአንድ ክብር አለማ አቅዶና አስቦ ሕይወትንም ጭምር መስጠት ማለት ነው…ህይወትንም ጭምር ቢሆን አጥቶ ሌላውን ለማኖር ቀድሞም አምኖና ወስኖ መተግበር ማለት ነው…
‹‹ልክ እንደ አርበኞቻችን ማለትሽ ነው….?››
‹‹አዎ እንደውም ዛሬ ለሀገር መስዋዕትነት ስለከፈሉ ሰዎች ምስጋና የምናቀርብበት ቀን አይደል…ሀገር ከምትደፈር የእኔ ህይወት ትቀጠፍ ብለው…ለልጆችና ለልጅ ልጆቻችን ባርነትን ከምናወርስ እኛ ዛሬ ደማችንን እረጭተን አጥንታችንን በትነን ነጻነትና ኩራትን እናወርሳቸው ብለው ታሪክ እንደሰሩት አባቶቻችን ነው መስዋዕትነት….ልክ እንደ በላይ ዘለቀ፡፡ ከገዛ አብራክ ልጅ ይልቅ ሀገርን ወይም ህዝብን ማስቀደም ማለት ነው…ለሀገር ክብር እና ለወገን መድህን ሆኖ መውደቅ ማለት ነው…ከስኬት በኃላም ላደረጉት ነገር የተለየ ክብር እና ሹመት አለመፈለግ ማለት ነው..ለሚወዱት ነገር ያለንን ነገር ሁሉ ህይወትንም ጭምር በነፃ መስጠት ማለት ነው….
እንደዛአይነት መስዋዕትነት ሚስጥሩ ከባድ ነው….ከድል በኃላ የበላይን ይሄንን ለሀገሩ በነፃ የሰጠውን መስዋዕትነት ሸፍጠኞቹ እና ባንዳዎቹ አልወደዱለትም ነበር..ምክንያም ስለእሱ ዝናና ታሪክ ሲሰሙ የእነሱን ሆዳምነት እና ትንሽነታቸውን በየጊዜው ስለሚያሳብቅባቸው ከንጉሱ አላትመው በአደባባይ እንዲሰቀል አደረጉት..ከጠላት በክብር የተረፈች ነፍሱ በገዛ ህዝቦቹ ምቀኝነት እና ክፍት ተነጠቀች…ይሄ ነው መስዋዕትነትን መራር የሚያደርገው…ለዚህ ነው መስዋዕትነት የሚለው ቃል ሚያስጠላኝ፡፡
‹‹ትክክል ነሽ ልጄ…ይሄ የበላይ ታሪክ የእንግሊዞች ቢሆን፤ይሄ የበላይ ታሪክ የአሜሪካኖች ቢሆን ኖሮ አንድ ሺ ፊልም እና አስር ሺ መጽሀፍ ተጽፎበት ነበር…?ስንት መንገድ እና ስንት ዩኒቨርሲቲ በስሙ ተሰይሞለት ነበር…?››
እኚህ ለሊቱን ከፕሮፌሰሩ ጋር በመጠጥ እያወራረድ በእሷ ለቅሷ ታጅበው ሲያወሩ ከነበሩት ነጥቦች ጥቂቶቹ ነበሩ..….
አሁን ሰዕቱ ከማለዳ 12፡45 ይላል…ፕሮፈሰሩ በመጠጥ እና በእሷ ወሬ ተዳክመው ይመስላል እዛው የተቀመጡበት ሶፋ ላይ ደገፍ እንደሉ እንቅልፍ ይዞቸው ጭልጥ ብሏል….ንስሯ ያለው መኝታ ቤት ውሰጥ ነው ከእሷ በላይ ትካዜና ቁዘማ ውስጥ ነው…ልትነካካው አልፈለገችም
እየተንገዳገደች እቤቱን ለቃ ወጣችና ወደ መኪና ማቆሚያ አመራች…‹‹ከጠጡ አይንዱ›› የሚለውን የትራፊኮችን ዋና ምክር አዘል መመሪያ ከቁብም ሳትቆጥር መኪናዋን አስነሳችና ግቢው ለቃ ተፈተለከች..ቀጥታ ወደመላኩ ቤት ነው ያመራችው…
እንደደረሰች ወደጊቢው አጥር አስጠጋችና መንገድ እንዳይዘጋ አስተካክላ መኪናዋን ካቆመች በኃላ ሞተሩን በማጥፋት ከመኪናዋ ወረደችና የግቢውን በራፍ መጥሪያ በሰከንድ ሽርፋራፊ ውስጥ ደጋግማ አንጣረረችው ፡፡ከጠበቀችው በፈጠነ ሁኔታ ተከፈተላተት..ከእንቅልፉ የባነነ እና በአንድ እጁ አይኖቹን እያሻሸ በሌላ እጁ የበራፍን እጄታ ይዞ ‹‹ምን ፈለግሽ….? ›› የሚላት ሰው ስትጠብቅ .. ንቁ እንቅልፍ በዓይኑ እንዳልዞረ የሚያስታውቅ..አይ እንደውም እያለቀሰ የነበረ ከዚህ በፊትም ያየችት ዘበኛ ከፈተላትና…ምንም ነገር ሳይጠይቃት እንድትገባ መንገዱን ዞር ብሎ ለቀቀለት …አልፋ ገባችና መንገዷን ቀጠለች ..በፍጥነት ዘግቷ ከኃላዋ ተከተላት፡፡
‹‹ዛሬ ምን አይነት ቀን ነው…….?ሰው ሁሉ ሲያለቅስ እንቅልፍ አጥቶ የሚያድርበት ቀን ነው እንዴ….?››ከዘበኛው ሁኔታ ተነስታ ውስጧን እየጠየቀች ነው… እራሷን ለመቆጣጠር በዚህ በተወለካከፈ እርምጃ አንድ ነገር አደናቅፏኝ እንዳትደፋ እየፈራች ስትራመድ ዘበኛው በታፈነ ድምጽ መናገር ጀመረ
‹‹ጋሼ ደውለውልሽ ነው….?››
‹‹አዎ›› አለችው….ምንም ሳታስብበት
‹‹አይ ቢጨንቃቸው እኮ ነው ..በቃ እኮ 10 ደቂቃም ዕድሜ አይራቸውም …አብቅቶላቸዋል…››
‹‹ማን ነው ያበቃለት ….?››ደንግጣ
👍94❤10🔥1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
የሰው ልጅ ውስጡ ሲጨልምበት እና የመጨረሻ ተስፋው መቁረጥ ላይ ሲደርስ ብስጭቱን የሚያራግፍበት ወይም የሚያላክክበት ሶስት አካላት አሉ…መንግስት፤እግዚያሔር እና እናት ፡፡
የመንግስት እንዝለለው…እግዚያብሄርን ግን ሲከፋን ለምን ፈጠርከኝ….? ብለን እንጠይቀዋለን……መፈጠር ትፈጊያለሽ ወይስ ይቅርብሽ ብለህ ምርጫ ሳትሰጠኝ ለምን ፈጠርከኝ…….?እሺ ይሁን ካለፍላጎቴ ከፈጠርከኝሽ በኋላ ለምን እንደፍላጎቴ ልታኖረኝ አልቻልክም.? ወይም ብትችል እንኳን ለምን አልፈለክም….? ብለን እንጠይቀዋለን…
እሱ በፍቃዱ እኛን መፍጠሩ እና እንደ እኛ ፍቃድ ሳይሆን እንደእራሱ ፍላጎትም የህይወት ጅረታችን የሚፈስበትን መስመር ማስመሩ ስህተት አይመስልም...የሰው ልጅም ሲበሳጭ ፤ተስፋ ሲቆርጥና ሲማረር ለምን ….?ብለን እሱን መጠየቃችንም ስህተት አይደለም….የእግዚያብሄር ዋናው ጥቅም የህይወት ሸክማችንን ከብዶን ስንንገዳገድ ከመውደቅ ታድጎ እንዲያግዘን እና የተሰበረ ተስፋችን እንዲጠግንልን የተንኮታኮተ ሞራላችን እንዲያክምልን ነው….ስለዚህ በከፋን ጊዜ ልንነጫነጭበት የግድ ነው…መነጫነጫችንም ክፋት የለውም፡፡
ከእግዜር ቀጥሎ በዚህ ጉዳይ የፈረደባት እናት ነች …አራት አመት ሆነን አርባ አመት ሁላችንም ውስጣችን ጨልሞ ነጋችንን ማለም ድክም ሲለን ወደ እናታችን ጉያ ሮጠን መሸጎጥ የመጀመሪያ ተግባራችን ነው፡፡
…እናታችንን በቅርብ አግኝተን የተመኘነውን ማድረግ ባንችል እንኳን ‹‹….እማዬ ለምን ወለድሺኝ….? ››ብለን ባትሰማንም ማማረራችን አይቀርም….በማማረሩ ውስጥ ምስጋና አለው…ለህልውናችን መሰረቷ ሰው ለመሆናችን ዋናዋ ምክንያቷ እሷ ለመሆኗ እየተናገርን ለዛም እውቅና እየሰጠናት ነው…
አሁን እነኬድሮን ያሉት ደሎመና ነው…ትውልድ ሀገሯ፡፡ያሉት ሳር ቤት ውስጥ ግድግዳውን ተደግፎ በተሰራ እና ግዙፍ አጎዛ በተነጠፈበት ትልቅ መደብ ላይ ፤ ንስሯን ከጉያዋ አድርጋ እናቷ እግሯ ላይ ተኝታ እንባዋን እያንጠባጠበች ነው….አሁን ካሉበት የሳር ቤት ፊት ለፊት ባለአራት ክፍል ቢላ ቤት ቢኖራትም እናቷ ግን አትወደውም…በቃ አስገዳጅ ሆኖባት እንግዳ ካልመጣባት በስተቀር ውሎዋ እዛች ሳር ቤት ውስጥ ነው…ምግቡ እዛው ይሰራል እዛው ብና ይፈላል….እዛው ጋደም ይባላል…
‹‹ገራኮ ማል ታቴ….?››(ሆዴ ምን ሆንሽ….?)ትጠይቃለች እናቷ
ድምጽ ያላጀበውን እንባዋን ከማፍሰስ ውጭ መልስ ልትሰጣት አልቻለችም….እርግጥ ሊሆን ያለውን ነገር ለእሷ ልትነግራት እና ልትሰናበታት ነው የመጣችው …ግን እንዲህ በቃላሉ ቃላት ከአንደበቷ ልታወጣ አልተቻላትም፡፡
‹‹ሆማ ኢንታኔ ሀርሜ ኮ..ነገኡማ ›( ….ምንም አልሆንኩ እናቴ…ደህና ነኝ)
‹‹ቀሮ ቲያ .ኢንሶቢን ….? ››(የእኔ ብልጥ አትዋሺኝ….?)
‹‹እማ ጨንቆኛል..በጣም ጨንቆኛል..መልሼ ወደሆድሽ ሁሉ መግባት አምሮኛል››
‹‹እኮ ንገሪኝ …እኔ እናትሽ እያለሁ ለማን ይድላው ብለሽ ትጨነቂያለሽ……?ደግሞ ባንቺ ጭንቀት አያምርም..አንቺ እኮ ለተጨነቀው ሁሉ መፍትሄ ስትሰጪ እንጂ ስትጨነቂ አያምርብሽም››
‹‹እማ አሁን የገጠመኝ ግን ከባድ ችግር ነው››
‹‹እኮ ምንድነው….?››
‹‹ልሄድ ነው››
ፈገግ አለች እናቷ‹‹እንቺ እኮ ገና ከልጅነትሽ ጡት ሳትጥይ ጀመሮ እንደሄድሽ ነው….ያንቺ መሄድ ምን አዲስ ነገር ኖሮት ነው
ሊያስጨንቅሽ የቻለው…….?አይዞሽ ልጄ ንስርሽ ከጎንሽ እስካለ የትም ብትሄጂ ምንም ሀሳብ አይገባኝም..በዛ ላይ የእኔ የእናትሽ ፀሎት እና የአባትሽ መንፈስ በየሄድሽበት ሁሉ ይከተልሻል… ይጠብቅሻል፡፡››
‹‹ሀርሜ…ንስሬ አብሮኝ አይሄድም ….››
ባለማመን አፍጥጣ አየችት..ምክንያቱም ንስሯ ለአንድም ቀን ቢሆን ከእሷ የተለየበትን አጋጣሚ እናቷ አታስታውስም..እንደውም እናቷ ሁለት መንታ ልጇች አሉኝ ብላ ነው የምታወራው…ያው እንደሚታወቀው እናቷ በምትኖርበት አካባቢ በጣም የተከበረችና ሰው ሁሉ የሚፈራት ነች‹‹….አረ ከዳቢሎስ የተወለደች ልጅ አለቻት …አንድ ነገር ብለን ብናስከፋ በልጇ ታስጠፋናለች….አታዩም እንዴ ልጇ እኮ አቅፋ የምትኖረውን ንስር ዳቢሎሱ አባቷ ነው የላከላት›› እያሉ በማንሾካሾክ እንደሚያሟት ታውቃለች……በዛም ምክንያት ሳይወዱ በግዳቸው ይፈሯታል..ስለሚፈሯትም በጣም ያከብሯታል….ግን ይህን ንስሯን የላከላት አባቷ መሆኑን ትጠራጠራለች እንጂ እርግጠኛ አይደለችም እንዴ….….?
‹‹ለምን ልጄ…?ለምንድነው አብሮሽ የማይሄደው….?››
‹‹የምሄድበት ቦታ እሱን ይዤ መሄድ አይፈቀድልኝም….ቢፈቀድልኝ እሱ አዛ መኖር አይችልም…. አየሩ አይስማማውም…››
ከተጋደመችበት ጭኖ ላይ ገፍትራ አስነሳቻትና እንድትቀመጥ አድርጋ ፊት ለፊት አፍጥጣ እያየቻት‹‹እንዴ ቅሪያ…እንዴት እሱን ጥለሽ መሄድ ታስቢያለሽ…….?የህይወት ጉዳይ ቢሆን እንኳን ማድረግ የለብሽም..እሱን ጥለሽ ሄድሽ ማለት እኔንም አሳዝነሽ ሄድሽ ማለት ነው…በዕድሜሽ ለመጀመሪያ ጊዜ አዝንብሻለሁ››
‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው›ይሏችኋል ይሄ ነው..ከእሷ ባሰች……በጣም ከባዱን ነገር ጭራሽ የበለጠ ጠጣር አደረገችባት፡፡
‹‹ሀርሜ ወዴት እንደምሄድ እኮ አልገባሽም….?››
‹‹ወደ የትም ይሁን አልኩሽ እኮ ..ንስርሽን ጥለሽ የትም መሄድ አትቺይም›› አለችና..ከእቅፌ ንስሬን መንጭቃ ወስዳ ጉያዋ ውስጥ ወሸቀችው…እሱም እጥፍጥፍ ብሎ ተሸጎጠላት፡፡
አፈረጠችው‹‹አባዬ ጋር ነው የምሄደው››
በእድሜዋ ሙሉ እናቷ በዚህ መጠን ስትደነግጥ አጋጥሞት አያውቅም..ሰው እንዴት እየታየ የሰውነት ቀለሙ እየተቀየረ ይሄዳል..?እንዴት እያያችሁት ደም ስሮቹ እየተወጣጠሩ እና ለእይታ ግልጽ እየሆኑ ይታያል….?ሰው እንዴት በሚያግለበልብ ሙቀት ውስጥ ሆኖ የአንታሪቲካ በረዶ ውስጥ እንደጣሉት ጥርሶቹ እርስ በርሳቸው ይንገጫገጫሉ….መልሰው ቃላት ለመለዋወጥ አያሌ ደቂቃዎች ነው ያሳለፈት…..
‹‹እንዴት አድረገሽ ነው የምትሄጂው….?››
‹‹ወገኖቹ ከስድስት ቀን በኃላ መጥተው ይወስዱኝል››
‹‹እሱስ ይመጣል….?››ጉጉት ባሰቃየው እይታ እያየች ጠየቀቻት
‹‹አይ እሱ እንዲመጣ የሚፈቅዱለት አይመስለኝ››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ…ግን እነሱስ እንደሚመጡ በምን አወቅሽ….?››
የሆነውን ሁሉ አስረዳቻት..ቀስ በቀስ በድንጋጤ ወይቦ የነበረው ፊቷ በደስታ እየደመቀ እና እየፈካ መጣ
‹‹እማ እየሳቅሽ እኮ ነው…….?››በገረሜታ ጠየቀቻት ..እያለቀሰችም እየሳቀችም መሆኗ ገርሞት
‹‹አዎ..በጣም ደስ ብሎኝ ነው››
‹‹እንዴ!! እንዴት ደስ ይልሻል..….?ከሄድኩ እኮ አልመለስም››
‹‹አውቃለሁ…ታውቂያለሽ አይደል ትናፍቂኛለሽ …. በጣም ነው የምወድሽ …ግን ወደአባትሽ ነው የምትሄጂው..ደግሞ በአንቺ ዕድሜ ሙሉ ለብቻዬ ተሸክሜው የኖርኩትን እወነቴን ዛሬ አንቺ አረጋገጥሺልኛል… እንዳልተሳሳትኩ አንቺ ልጄ ምስክር ነሽ…እንቡጥ ልጃገረድ ሆኜ ከሌላ አለም የመጣ ሰው መሰል ፍጡር አፍቅሬ እንደነበረ ….ወደእሱ የመኖሬያ አለምም ለአንድ ቀን ወስዶኝ እንደነበረ…የወለድኳት ልጅ አባትም እሱ እንደሆነ ለዘመድም ለጓደኞቼም ሳወራ ነበር የኖርኩት..ግን አውቃለሁ አንድም ሰው አምኖኝ አያውቅም ነበር…እንደውም ነካ እንደሚያደርግኝ ነው የሚስቡት…ዛሬ እወነቴን እንደነበርና ዕድሜዬን ሙሉ ያፈቀርኩት ፍቅር የእውነት እንደነበር አንቺም ተገንዝበኛል…በህይወቴ ሙሉ ከዚህ በላይ ምንም የሚያስደስተኝ ነገር ሊፈጠር አይችልም››
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
የሰው ልጅ ውስጡ ሲጨልምበት እና የመጨረሻ ተስፋው መቁረጥ ላይ ሲደርስ ብስጭቱን የሚያራግፍበት ወይም የሚያላክክበት ሶስት አካላት አሉ…መንግስት፤እግዚያሔር እና እናት ፡፡
የመንግስት እንዝለለው…እግዚያብሄርን ግን ሲከፋን ለምን ፈጠርከኝ….? ብለን እንጠይቀዋለን……መፈጠር ትፈጊያለሽ ወይስ ይቅርብሽ ብለህ ምርጫ ሳትሰጠኝ ለምን ፈጠርከኝ…….?እሺ ይሁን ካለፍላጎቴ ከፈጠርከኝሽ በኋላ ለምን እንደፍላጎቴ ልታኖረኝ አልቻልክም.? ወይም ብትችል እንኳን ለምን አልፈለክም….? ብለን እንጠይቀዋለን…
እሱ በፍቃዱ እኛን መፍጠሩ እና እንደ እኛ ፍቃድ ሳይሆን እንደእራሱ ፍላጎትም የህይወት ጅረታችን የሚፈስበትን መስመር ማስመሩ ስህተት አይመስልም...የሰው ልጅም ሲበሳጭ ፤ተስፋ ሲቆርጥና ሲማረር ለምን ….?ብለን እሱን መጠየቃችንም ስህተት አይደለም….የእግዚያብሄር ዋናው ጥቅም የህይወት ሸክማችንን ከብዶን ስንንገዳገድ ከመውደቅ ታድጎ እንዲያግዘን እና የተሰበረ ተስፋችን እንዲጠግንልን የተንኮታኮተ ሞራላችን እንዲያክምልን ነው….ስለዚህ በከፋን ጊዜ ልንነጫነጭበት የግድ ነው…መነጫነጫችንም ክፋት የለውም፡፡
ከእግዜር ቀጥሎ በዚህ ጉዳይ የፈረደባት እናት ነች …አራት አመት ሆነን አርባ አመት ሁላችንም ውስጣችን ጨልሞ ነጋችንን ማለም ድክም ሲለን ወደ እናታችን ጉያ ሮጠን መሸጎጥ የመጀመሪያ ተግባራችን ነው፡፡
…እናታችንን በቅርብ አግኝተን የተመኘነውን ማድረግ ባንችል እንኳን ‹‹….እማዬ ለምን ወለድሺኝ….? ››ብለን ባትሰማንም ማማረራችን አይቀርም….በማማረሩ ውስጥ ምስጋና አለው…ለህልውናችን መሰረቷ ሰው ለመሆናችን ዋናዋ ምክንያቷ እሷ ለመሆኗ እየተናገርን ለዛም እውቅና እየሰጠናት ነው…
አሁን እነኬድሮን ያሉት ደሎመና ነው…ትውልድ ሀገሯ፡፡ያሉት ሳር ቤት ውስጥ ግድግዳውን ተደግፎ በተሰራ እና ግዙፍ አጎዛ በተነጠፈበት ትልቅ መደብ ላይ ፤ ንስሯን ከጉያዋ አድርጋ እናቷ እግሯ ላይ ተኝታ እንባዋን እያንጠባጠበች ነው….አሁን ካሉበት የሳር ቤት ፊት ለፊት ባለአራት ክፍል ቢላ ቤት ቢኖራትም እናቷ ግን አትወደውም…በቃ አስገዳጅ ሆኖባት እንግዳ ካልመጣባት በስተቀር ውሎዋ እዛች ሳር ቤት ውስጥ ነው…ምግቡ እዛው ይሰራል እዛው ብና ይፈላል….እዛው ጋደም ይባላል…
‹‹ገራኮ ማል ታቴ….?››(ሆዴ ምን ሆንሽ….?)ትጠይቃለች እናቷ
ድምጽ ያላጀበውን እንባዋን ከማፍሰስ ውጭ መልስ ልትሰጣት አልቻለችም….እርግጥ ሊሆን ያለውን ነገር ለእሷ ልትነግራት እና ልትሰናበታት ነው የመጣችው …ግን እንዲህ በቃላሉ ቃላት ከአንደበቷ ልታወጣ አልተቻላትም፡፡
‹‹ሆማ ኢንታኔ ሀርሜ ኮ..ነገኡማ ›( ….ምንም አልሆንኩ እናቴ…ደህና ነኝ)
‹‹ቀሮ ቲያ .ኢንሶቢን ….? ››(የእኔ ብልጥ አትዋሺኝ….?)
‹‹እማ ጨንቆኛል..በጣም ጨንቆኛል..መልሼ ወደሆድሽ ሁሉ መግባት አምሮኛል››
‹‹እኮ ንገሪኝ …እኔ እናትሽ እያለሁ ለማን ይድላው ብለሽ ትጨነቂያለሽ……?ደግሞ ባንቺ ጭንቀት አያምርም..አንቺ እኮ ለተጨነቀው ሁሉ መፍትሄ ስትሰጪ እንጂ ስትጨነቂ አያምርብሽም››
‹‹እማ አሁን የገጠመኝ ግን ከባድ ችግር ነው››
‹‹እኮ ምንድነው….?››
‹‹ልሄድ ነው››
ፈገግ አለች እናቷ‹‹እንቺ እኮ ገና ከልጅነትሽ ጡት ሳትጥይ ጀመሮ እንደሄድሽ ነው….ያንቺ መሄድ ምን አዲስ ነገር ኖሮት ነው
ሊያስጨንቅሽ የቻለው…….?አይዞሽ ልጄ ንስርሽ ከጎንሽ እስካለ የትም ብትሄጂ ምንም ሀሳብ አይገባኝም..በዛ ላይ የእኔ የእናትሽ ፀሎት እና የአባትሽ መንፈስ በየሄድሽበት ሁሉ ይከተልሻል… ይጠብቅሻል፡፡››
‹‹ሀርሜ…ንስሬ አብሮኝ አይሄድም ….››
ባለማመን አፍጥጣ አየችት..ምክንያቱም ንስሯ ለአንድም ቀን ቢሆን ከእሷ የተለየበትን አጋጣሚ እናቷ አታስታውስም..እንደውም እናቷ ሁለት መንታ ልጇች አሉኝ ብላ ነው የምታወራው…ያው እንደሚታወቀው እናቷ በምትኖርበት አካባቢ በጣም የተከበረችና ሰው ሁሉ የሚፈራት ነች‹‹….አረ ከዳቢሎስ የተወለደች ልጅ አለቻት …አንድ ነገር ብለን ብናስከፋ በልጇ ታስጠፋናለች….አታዩም እንዴ ልጇ እኮ አቅፋ የምትኖረውን ንስር ዳቢሎሱ አባቷ ነው የላከላት›› እያሉ በማንሾካሾክ እንደሚያሟት ታውቃለች……በዛም ምክንያት ሳይወዱ በግዳቸው ይፈሯታል..ስለሚፈሯትም በጣም ያከብሯታል….ግን ይህን ንስሯን የላከላት አባቷ መሆኑን ትጠራጠራለች እንጂ እርግጠኛ አይደለችም እንዴ….….?
‹‹ለምን ልጄ…?ለምንድነው አብሮሽ የማይሄደው….?››
‹‹የምሄድበት ቦታ እሱን ይዤ መሄድ አይፈቀድልኝም….ቢፈቀድልኝ እሱ አዛ መኖር አይችልም…. አየሩ አይስማማውም…››
ከተጋደመችበት ጭኖ ላይ ገፍትራ አስነሳቻትና እንድትቀመጥ አድርጋ ፊት ለፊት አፍጥጣ እያየቻት‹‹እንዴ ቅሪያ…እንዴት እሱን ጥለሽ መሄድ ታስቢያለሽ…….?የህይወት ጉዳይ ቢሆን እንኳን ማድረግ የለብሽም..እሱን ጥለሽ ሄድሽ ማለት እኔንም አሳዝነሽ ሄድሽ ማለት ነው…በዕድሜሽ ለመጀመሪያ ጊዜ አዝንብሻለሁ››
‹‹ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው›ይሏችኋል ይሄ ነው..ከእሷ ባሰች……በጣም ከባዱን ነገር ጭራሽ የበለጠ ጠጣር አደረገችባት፡፡
‹‹ሀርሜ ወዴት እንደምሄድ እኮ አልገባሽም….?››
‹‹ወደ የትም ይሁን አልኩሽ እኮ ..ንስርሽን ጥለሽ የትም መሄድ አትቺይም›› አለችና..ከእቅፌ ንስሬን መንጭቃ ወስዳ ጉያዋ ውስጥ ወሸቀችው…እሱም እጥፍጥፍ ብሎ ተሸጎጠላት፡፡
አፈረጠችው‹‹አባዬ ጋር ነው የምሄደው››
በእድሜዋ ሙሉ እናቷ በዚህ መጠን ስትደነግጥ አጋጥሞት አያውቅም..ሰው እንዴት እየታየ የሰውነት ቀለሙ እየተቀየረ ይሄዳል..?እንዴት እያያችሁት ደም ስሮቹ እየተወጣጠሩ እና ለእይታ ግልጽ እየሆኑ ይታያል….?ሰው እንዴት በሚያግለበልብ ሙቀት ውስጥ ሆኖ የአንታሪቲካ በረዶ ውስጥ እንደጣሉት ጥርሶቹ እርስ በርሳቸው ይንገጫገጫሉ….መልሰው ቃላት ለመለዋወጥ አያሌ ደቂቃዎች ነው ያሳለፈት…..
‹‹እንዴት አድረገሽ ነው የምትሄጂው….?››
‹‹ወገኖቹ ከስድስት ቀን በኃላ መጥተው ይወስዱኝል››
‹‹እሱስ ይመጣል….?››ጉጉት ባሰቃየው እይታ እያየች ጠየቀቻት
‹‹አይ እሱ እንዲመጣ የሚፈቅዱለት አይመስለኝ››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ…ግን እነሱስ እንደሚመጡ በምን አወቅሽ….?››
የሆነውን ሁሉ አስረዳቻት..ቀስ በቀስ በድንጋጤ ወይቦ የነበረው ፊቷ በደስታ እየደመቀ እና እየፈካ መጣ
‹‹እማ እየሳቅሽ እኮ ነው…….?››በገረሜታ ጠየቀቻት ..እያለቀሰችም እየሳቀችም መሆኗ ገርሞት
‹‹አዎ..በጣም ደስ ብሎኝ ነው››
‹‹እንዴ!! እንዴት ደስ ይልሻል..….?ከሄድኩ እኮ አልመለስም››
‹‹አውቃለሁ…ታውቂያለሽ አይደል ትናፍቂኛለሽ …. በጣም ነው የምወድሽ …ግን ወደአባትሽ ነው የምትሄጂው..ደግሞ በአንቺ ዕድሜ ሙሉ ለብቻዬ ተሸክሜው የኖርኩትን እወነቴን ዛሬ አንቺ አረጋገጥሺልኛል… እንዳልተሳሳትኩ አንቺ ልጄ ምስክር ነሽ…እንቡጥ ልጃገረድ ሆኜ ከሌላ አለም የመጣ ሰው መሰል ፍጡር አፍቅሬ እንደነበረ ….ወደእሱ የመኖሬያ አለምም ለአንድ ቀን ወስዶኝ እንደነበረ…የወለድኳት ልጅ አባትም እሱ እንደሆነ ለዘመድም ለጓደኞቼም ሳወራ ነበር የኖርኩት..ግን አውቃለሁ አንድም ሰው አምኖኝ አያውቅም ነበር…እንደውም ነካ እንደሚያደርግኝ ነው የሚስቡት…ዛሬ እወነቴን እንደነበርና ዕድሜዬን ሙሉ ያፈቀርኩት ፍቅር የእውነት እንደነበር አንቺም ተገንዝበኛል…በህይወቴ ሙሉ ከዚህ በላይ ምንም የሚያስደስተኝ ነገር ሊፈጠር አይችልም››
👍106❤10🥰1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/////
ወደሸገር ተመልሰዋል..ማለት እሷ እና ንስሯ ፡፡ለእናቷ በመጨረሻው ቀን ተመልሳ እንደምታያትና ወደአባቷ ዘመዶችም በምትሄድበት ቀን አጠገቧ እንድትሆን እንደምትፈልግ ነግራትና ቃል ገብታላት ነው የመጣችው፡፡
እስከዛው ያሉትን ቀጣዬቹን በስስት እየተሸራረፉ በመርገፍና በማለቅ ላይ ያሉትን ቀሪ 5 የሰቀቀን ቀናቶችን ሸገር ልታሳልፍ ወስናለች….ምን አልባትም አይታውቅም… በመሀል ሀሳቧን ልትቀይር ትችላለች፡፡
ግን አሁን ተረጋግታ እቤቷ መቀመጥ አልቻለችም … ሰዓቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ቢያልፍም ልትቆጣጠረው የማትችለው ከውስጧ ሚመነጭ ስውር ስሜት ውጪ ውጪ ይላት ጀመር….ልብሷን ቀያየረችና መኪናዋን ወዳለችበት መራመድ ከጀመረች በኃላ ሀሳቧን ቀየረችና ስልኳን አውጥታ ደወለች..አዎ ነፃ መሆን ነው የምትፈልገው….ላዳ ያለው የምታውቀው ልጅ ጋር ነው የደወለችው፡፡
‹‹ሄሎ››
‹‹ሰላም ነው… .ፈልጌህ ነበር…የት ነህ ያለኸው?››
‹‹ይቅርታ ዛሬ ስራ ላይ አይደለሁም መኪናዬ ተበላሽታ ገራዥ ነች››
‹‹በቃ አንተ ናልኛ ..የእኔ መኪና ስላለች ትይዝልኛለህ …ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ መንዳት አልፈለኩም››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር.. ግን ያው ስራ የለኝም ብዬ ከከተማ ወጣ ብያለሁ…..ከፈለግሽ አንድ ጓደኛዬን ልልክልሽ እችላለሁ››
‹‹ደስ ይለኛል››
‹‹በቃ ንገረውና ቁጥርሽን ሰጠዋለሁ…ይደውልልሻል››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ››ስልኳን ዘጋችውና ጊቢዋ ውስጥ እየተዘዋወረች እስኪደወልላት መጠበቅ ጀመረች….፡፡
ብዙም ሳይቆይ ስልኳ ላይ የማታውቀው ቁጥር ተንጫረረ …አነሳችው..አናገረችው ….በ15 ደቂቃ እንደሚደርስ ነገራት…..መጠበቅ ጀመረች…..
‹‹አዎ በዚህ ለሊት ምን አልባት ለመጨረሻ ጊዜ ማበድ እፈልጋለሁ..አዎ ብዙ ነገር ማድረግ አምሮኛል…የማሰብ አቅሜን አዳክሞ ጭንቀቴን የሚቀንስልኝን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ እፈልጋለሁ…..መጠጣትና መስከር …መቁላላትና መዋሰብ እፈልጋለሁ…መጣላትና መደባደብም ካገኘሁ አልጠላም…››
እግዜር ይስጠው የመኪና ጥሩንባ ድምጽ ሰማች...ጎበዝ ልጅ ነው… በነገረችው ምልክት መሰረት ሳይሳሳት መምጣቱ አስደሰታት… በራፍን ከፈተችና ወጣች…በምልክት ጠራት … የላዳውን በራፍ ከፈተላትና ገባች፡፡
‹‹ወዴት ልውሰድሽ….?››
‹‹መጠጣት ነው የምፈልገው››አለችው፡፡
‹‹መጠጣት›› አላት ግራ ተጋብቶ፡፡
‹‹መጠጣት ስልህ …ብሽቅጥ እስክል መጠጣት ነው የምፈልገው…የፈለከውን ያህል ከፍልሀለሁ እስከንጋትም ቢሆን አብረኸኝ ትቆይና እቤቴ ታስገባኛለህ››
‹‹ይመችሽ ››አላት….
እንዲሁ ወደደችው…አንድን ሰው አይተን በውስጣችን ስለሰውዬው ደስ የሚል ስሜት ሲሰማን ውቃቢዬ ወዶታል የምንለው ነገር አለ አይደል..….? እሷም ይሄን የላዳ ሹፌር እንዳየችው እንደዛ ነው የተሰማት፡፡
‹‹ምርጫሽ የት አካባቢ ነው?››
‹‹የፈለክበት ውሰደኝ ››
‹‹ቺቺኚያ ይመችሻል››
‹‹ይመችህ››
ነዳው….ንስሯ አምኗት እቤት ሊቀር አልቻለም …ከፊት ለፊታቸው በላዳዋ ፍጥነት መጠን ሲበር በመኪናዋ መስታወት አሻግራ አየችው….
ደረሱና መኪናዋን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀበት ቦታ ፓርክ አድርገው አንዱ ጭፈራ ቤት ገቡ……እሷ ደረቅ አልኮለሏን ስታዝ እሱ ዉሀ አዘዘ..
‹‹ለምን ትንሽ አትሞከርም….? ››
‹‹አይ …የሞያዬ ስነምግባር አይፈቅድልኝም›› ሲል መለሰላት በቀልድ መልክ
..ዝም አለችው… በላይ በላዩ መለጋቱን ቀጠለች….የሙዚቃው ከጣሪያ በላይ ጩኸት…የለሊት ንገስታቶች በገዢ መሳይ ወንዶች ዙሪያ መሽከርከር፤ በስካር የሚናውዙና የሚደንሱ ወንዶችና ሴቶች የሆቴሉን ወለል መሙላት…የሆነ ትርምስምስ ያለ ነገር ነው የሚታየው….በዛ ላይ መብራቱ በአምስት አይነት ቀለም በመፈራረቅ ቦግ ብልጭ ሲል እይታን ብዥ ያደርጋል…….ግን በምትፈልገው መጠን ባይሆንም ተመችቷታል ፡፡ቢሆንም ደስታዋን ሙሉ ማድረግ ፈለገች…
‹‹ሌላ ጓደኛ የለህም….?››ድንገት ከመሬት ተነስታ ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን አይነት….?››
‹‹ሹፌር››..
‹‹ምን ያደርግልሻል….?››
‹‹ያንተን መኪና የሚነዳልን››
‹‹እኔስ….?››አላት በጥያቄዋ ግራ ተጋብቶ
‹‹አይ አንተማ እንድታጣጣኝ ፈልጌ ነው..ብቻዬን ደበረኝ››
‹‹እ ..ቆይ እስኪ ደዋውዬ ልሞክር››አለና ስልኩን እየጎረጎረ ከሆቴሉ ወጣ..ሲወጣ ከጀርባው ሳታየው ነበር…ቁመናው መስጧታል..በቃ የተለመደው ችግሯ እያገረሸባት ነው..ጭኗ መካከል አሳከካት…ምን አይነት መጥፎ አመል ነው…እዛም አባቷ አለም ስትሄድ እንዲህ የሚበላት ነገር ወቅት እየጠበቀ ይፈታተናት ይሆን እንደዛ ከሆነ ምንድነው የምታደርገው….….?
ሀሳቧን ሳትጨርስ መጣና መቀመጫው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ..‹‹ተሳክቶል…ተቀላቅዬሻለሁ››አላት
በደስታ እየፈገገች‹‹ምን ይምጣልህ..?››ሥትል ምርጫውን ጠየቀችው፡፡
‹‹አንቺ የያዝሺውን…››
ሙሉ ጠርሙስ አዘዙ…መጣላቸው…… ይገለብጡት ጀመረ…እየደነሱ እየተቀመጡ …ደግሞ ተመልሰው በመነሳት እየደነሱ ..ውልቅልቃቸው እስኪወጣ ድረስ አስነኩት‹‹ …አቤት ዳንሱ !!ፕሮፌሽናል ነው ፡፡ልቤን ስልብ ነው ያደረገኝ…›አለች በዳንስ ችሎታው ተመስጣ፡፡ይበልጥ ሰውነቱ ላይ ተለጥፋ በተሸሻችው መጠን የጭኗ መብላላ አደብ እየነሳት ነው…በትርምሱ መካከል በዳንስ ስልት በማሳበብ እጣቷን ወደጭኗ በመስደድ ይሉኝታ እስክታጣ ድረስ እያሻሸች ነው..ደግነቱ ሁሉም በመጠጥ የደመቀ እና በመብራቱ ቦግ ብልጭ ብዥ ያለበት መሆኑ በጃት …
ከለሊቱ አምስት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ግን ተዳከሙ…
‹‹ቤት እንቀይር ….?››አለችው… ቤት መቀየር የፈለገችው ሙዳችውንም ጭምር መቀየር ስለፈለገች ነው… ተስማማ ..ሂሳብ ዘግተው ወጡ…
‹‹ጭፈራ ቤት ሳይሆን ዝም ብለን የምንጠጣበት ቦታ ነው የምፈልገው…››
ወደላዳዋ ይዟት ሄደ …ቅድም ተጠርቶ የመጣው ጓዳኛውን ገቢና ቁጭ ብሎ ጫቱን ሲቀመቅም አገኙት..ሁለቱም ተደጋግፈው ከኃላ ገቡ… ላዳዋ ተንቀሳቀሰች… በመስኮቱ አንጋጣ ሰማዮን ሰታይ ንስሯን ቀድሟት ለመብረር ሲያኮበኩብ አየችው…ሰካራሙ ጓደኛው እይታዋን ተከትሎ ወደውጭ በተመሳሳይ ሁኔታ ካየ በኃላ‹‹ አይገርምም ይሄ አሞራ ቅድምም ስንመጣ ከፊት ለፊታችን ሲበር ነበር….እርግጠኛ ነኝ የተለየ ከለር ስላለው አስተውዬው ነበር››አለ
‹‹አሞራ አይደለም..ንስር ነው››አረመችው
‹‹እንዴ.. አዎ ንስር ነው ትክክል ..አንቺ ግን እንዴት አወቅሽ….?››
‹‹የእኔ ነው››በልበ ሙሉነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእኔ ነው ስትይ….?››ያዝ ያዝ በሚያደርገው የስካር አንደበት ጠየቃት
‹‹ወንድሜ ነው››
ሁለቱም ተንከትክተው ሳቁ
‹‹..ቀልደኛ ነሽ..ይበልጥ ስትጠጪ ደግሞ ይብልጥ ቀልደኛ የመሆን ተስፋ አለሽ ማለት ነው››አላት፡፡
….አስረድቶ ማሰማንም ሆነ ተከራክሮ ማሸንፈ እንደማትችል ስለተረዳች‹‹ይሁንልህ›› አለችው ፡፡
መገናኛ አካባቢ ደርሱ… ብዙም ትርምስ የሌለበት እሷ የማታውቀው ሁለቱ ግን የሚያውቁት ሆቴል ይዘዋት ገቡ..ሹፌሩ ከላዳዋ አልወረደም…‹‹ጫቴን ብቅም ይሻለኝል›› ብሎ ቀረ …እነሱ ተያይዘው ገቡና የተገነጠለ እና ከታዳሚ የራቀ ወንበር ይዘው ተቀመጡ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/////
ወደሸገር ተመልሰዋል..ማለት እሷ እና ንስሯ ፡፡ለእናቷ በመጨረሻው ቀን ተመልሳ እንደምታያትና ወደአባቷ ዘመዶችም በምትሄድበት ቀን አጠገቧ እንድትሆን እንደምትፈልግ ነግራትና ቃል ገብታላት ነው የመጣችው፡፡
እስከዛው ያሉትን ቀጣዬቹን በስስት እየተሸራረፉ በመርገፍና በማለቅ ላይ ያሉትን ቀሪ 5 የሰቀቀን ቀናቶችን ሸገር ልታሳልፍ ወስናለች….ምን አልባትም አይታውቅም… በመሀል ሀሳቧን ልትቀይር ትችላለች፡፡
ግን አሁን ተረጋግታ እቤቷ መቀመጥ አልቻለችም … ሰዓቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ቢያልፍም ልትቆጣጠረው የማትችለው ከውስጧ ሚመነጭ ስውር ስሜት ውጪ ውጪ ይላት ጀመር….ልብሷን ቀያየረችና መኪናዋን ወዳለችበት መራመድ ከጀመረች በኃላ ሀሳቧን ቀየረችና ስልኳን አውጥታ ደወለች..አዎ ነፃ መሆን ነው የምትፈልገው….ላዳ ያለው የምታውቀው ልጅ ጋር ነው የደወለችው፡፡
‹‹ሄሎ››
‹‹ሰላም ነው… .ፈልጌህ ነበር…የት ነህ ያለኸው?››
‹‹ይቅርታ ዛሬ ስራ ላይ አይደለሁም መኪናዬ ተበላሽታ ገራዥ ነች››
‹‹በቃ አንተ ናልኛ ..የእኔ መኪና ስላለች ትይዝልኛለህ …ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ መንዳት አልፈለኩም››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር.. ግን ያው ስራ የለኝም ብዬ ከከተማ ወጣ ብያለሁ…..ከፈለግሽ አንድ ጓደኛዬን ልልክልሽ እችላለሁ››
‹‹ደስ ይለኛል››
‹‹በቃ ንገረውና ቁጥርሽን ሰጠዋለሁ…ይደውልልሻል››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ››ስልኳን ዘጋችውና ጊቢዋ ውስጥ እየተዘዋወረች እስኪደወልላት መጠበቅ ጀመረች….፡፡
ብዙም ሳይቆይ ስልኳ ላይ የማታውቀው ቁጥር ተንጫረረ …አነሳችው..አናገረችው ….በ15 ደቂቃ እንደሚደርስ ነገራት…..መጠበቅ ጀመረች…..
‹‹አዎ በዚህ ለሊት ምን አልባት ለመጨረሻ ጊዜ ማበድ እፈልጋለሁ..አዎ ብዙ ነገር ማድረግ አምሮኛል…የማሰብ አቅሜን አዳክሞ ጭንቀቴን የሚቀንስልኝን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ እፈልጋለሁ…..መጠጣትና መስከር …መቁላላትና መዋሰብ እፈልጋለሁ…መጣላትና መደባደብም ካገኘሁ አልጠላም…››
እግዜር ይስጠው የመኪና ጥሩንባ ድምጽ ሰማች...ጎበዝ ልጅ ነው… በነገረችው ምልክት መሰረት ሳይሳሳት መምጣቱ አስደሰታት… በራፍን ከፈተችና ወጣች…በምልክት ጠራት … የላዳውን በራፍ ከፈተላትና ገባች፡፡
‹‹ወዴት ልውሰድሽ….?››
‹‹መጠጣት ነው የምፈልገው››አለችው፡፡
‹‹መጠጣት›› አላት ግራ ተጋብቶ፡፡
‹‹መጠጣት ስልህ …ብሽቅጥ እስክል መጠጣት ነው የምፈልገው…የፈለከውን ያህል ከፍልሀለሁ እስከንጋትም ቢሆን አብረኸኝ ትቆይና እቤቴ ታስገባኛለህ››
‹‹ይመችሽ ››አላት….
እንዲሁ ወደደችው…አንድን ሰው አይተን በውስጣችን ስለሰውዬው ደስ የሚል ስሜት ሲሰማን ውቃቢዬ ወዶታል የምንለው ነገር አለ አይደል..….? እሷም ይሄን የላዳ ሹፌር እንዳየችው እንደዛ ነው የተሰማት፡፡
‹‹ምርጫሽ የት አካባቢ ነው?››
‹‹የፈለክበት ውሰደኝ ››
‹‹ቺቺኚያ ይመችሻል››
‹‹ይመችህ››
ነዳው….ንስሯ አምኗት እቤት ሊቀር አልቻለም …ከፊት ለፊታቸው በላዳዋ ፍጥነት መጠን ሲበር በመኪናዋ መስታወት አሻግራ አየችው….
ደረሱና መኪናዋን ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀበት ቦታ ፓርክ አድርገው አንዱ ጭፈራ ቤት ገቡ……እሷ ደረቅ አልኮለሏን ስታዝ እሱ ዉሀ አዘዘ..
‹‹ለምን ትንሽ አትሞከርም….? ››
‹‹አይ …የሞያዬ ስነምግባር አይፈቅድልኝም›› ሲል መለሰላት በቀልድ መልክ
..ዝም አለችው… በላይ በላዩ መለጋቱን ቀጠለች….የሙዚቃው ከጣሪያ በላይ ጩኸት…የለሊት ንገስታቶች በገዢ መሳይ ወንዶች ዙሪያ መሽከርከር፤ በስካር የሚናውዙና የሚደንሱ ወንዶችና ሴቶች የሆቴሉን ወለል መሙላት…የሆነ ትርምስምስ ያለ ነገር ነው የሚታየው….በዛ ላይ መብራቱ በአምስት አይነት ቀለም በመፈራረቅ ቦግ ብልጭ ሲል እይታን ብዥ ያደርጋል…….ግን በምትፈልገው መጠን ባይሆንም ተመችቷታል ፡፡ቢሆንም ደስታዋን ሙሉ ማድረግ ፈለገች…
‹‹ሌላ ጓደኛ የለህም….?››ድንገት ከመሬት ተነስታ ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን አይነት….?››
‹‹ሹፌር››..
‹‹ምን ያደርግልሻል….?››
‹‹ያንተን መኪና የሚነዳልን››
‹‹እኔስ….?››አላት በጥያቄዋ ግራ ተጋብቶ
‹‹አይ አንተማ እንድታጣጣኝ ፈልጌ ነው..ብቻዬን ደበረኝ››
‹‹እ ..ቆይ እስኪ ደዋውዬ ልሞክር››አለና ስልኩን እየጎረጎረ ከሆቴሉ ወጣ..ሲወጣ ከጀርባው ሳታየው ነበር…ቁመናው መስጧታል..በቃ የተለመደው ችግሯ እያገረሸባት ነው..ጭኗ መካከል አሳከካት…ምን አይነት መጥፎ አመል ነው…እዛም አባቷ አለም ስትሄድ እንዲህ የሚበላት ነገር ወቅት እየጠበቀ ይፈታተናት ይሆን እንደዛ ከሆነ ምንድነው የምታደርገው….….?
ሀሳቧን ሳትጨርስ መጣና መቀመጫው ላይ ተመልሶ እየተቀመጠ..‹‹ተሳክቶል…ተቀላቅዬሻለሁ››አላት
በደስታ እየፈገገች‹‹ምን ይምጣልህ..?››ሥትል ምርጫውን ጠየቀችው፡፡
‹‹አንቺ የያዝሺውን…››
ሙሉ ጠርሙስ አዘዙ…መጣላቸው…… ይገለብጡት ጀመረ…እየደነሱ እየተቀመጡ …ደግሞ ተመልሰው በመነሳት እየደነሱ ..ውልቅልቃቸው እስኪወጣ ድረስ አስነኩት‹‹ …አቤት ዳንሱ !!ፕሮፌሽናል ነው ፡፡ልቤን ስልብ ነው ያደረገኝ…›አለች በዳንስ ችሎታው ተመስጣ፡፡ይበልጥ ሰውነቱ ላይ ተለጥፋ በተሸሻችው መጠን የጭኗ መብላላ አደብ እየነሳት ነው…በትርምሱ መካከል በዳንስ ስልት በማሳበብ እጣቷን ወደጭኗ በመስደድ ይሉኝታ እስክታጣ ድረስ እያሻሸች ነው..ደግነቱ ሁሉም በመጠጥ የደመቀ እና በመብራቱ ቦግ ብልጭ ብዥ ያለበት መሆኑ በጃት …
ከለሊቱ አምስት ሰዓት አካባቢ ሲሆን ግን ተዳከሙ…
‹‹ቤት እንቀይር ….?››አለችው… ቤት መቀየር የፈለገችው ሙዳችውንም ጭምር መቀየር ስለፈለገች ነው… ተስማማ ..ሂሳብ ዘግተው ወጡ…
‹‹ጭፈራ ቤት ሳይሆን ዝም ብለን የምንጠጣበት ቦታ ነው የምፈልገው…››
ወደላዳዋ ይዟት ሄደ …ቅድም ተጠርቶ የመጣው ጓዳኛውን ገቢና ቁጭ ብሎ ጫቱን ሲቀመቅም አገኙት..ሁለቱም ተደጋግፈው ከኃላ ገቡ… ላዳዋ ተንቀሳቀሰች… በመስኮቱ አንጋጣ ሰማዮን ሰታይ ንስሯን ቀድሟት ለመብረር ሲያኮበኩብ አየችው…ሰካራሙ ጓደኛው እይታዋን ተከትሎ ወደውጭ በተመሳሳይ ሁኔታ ካየ በኃላ‹‹ አይገርምም ይሄ አሞራ ቅድምም ስንመጣ ከፊት ለፊታችን ሲበር ነበር….እርግጠኛ ነኝ የተለየ ከለር ስላለው አስተውዬው ነበር››አለ
‹‹አሞራ አይደለም..ንስር ነው››አረመችው
‹‹እንዴ.. አዎ ንስር ነው ትክክል ..አንቺ ግን እንዴት አወቅሽ….?››
‹‹የእኔ ነው››በልበ ሙሉነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእኔ ነው ስትይ….?››ያዝ ያዝ በሚያደርገው የስካር አንደበት ጠየቃት
‹‹ወንድሜ ነው››
ሁለቱም ተንከትክተው ሳቁ
‹‹..ቀልደኛ ነሽ..ይበልጥ ስትጠጪ ደግሞ ይብልጥ ቀልደኛ የመሆን ተስፋ አለሽ ማለት ነው››አላት፡፡
….አስረድቶ ማሰማንም ሆነ ተከራክሮ ማሸንፈ እንደማትችል ስለተረዳች‹‹ይሁንልህ›› አለችው ፡፡
መገናኛ አካባቢ ደርሱ… ብዙም ትርምስ የሌለበት እሷ የማታውቀው ሁለቱ ግን የሚያውቁት ሆቴል ይዘዋት ገቡ..ሹፌሩ ከላዳዋ አልወረደም…‹‹ጫቴን ብቅም ይሻለኝል›› ብሎ ቀረ …እነሱ ተያይዘው ገቡና የተገነጠለ እና ከታዳሚ የራቀ ወንበር ይዘው ተቀመጡ፡፡
👍86❤11😁2👎1🤔1😱1😢1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹ለማንኛውም ልድገምልሽ ኤርምያስ እባላለሁ…ለ15 ዓመት ያህል በማንዴላ ሀገር በሆነችው ደቡቡ አፍሪካ ጀሆንስበርግ ኖሬያለሁ… ወደሀገሬ ከተመለስኩ ሁለት ዓመት ከግማሽ ሆኖኛል፡፡የ20ዓመት አፍላ ፍንዳታ ሆኜ ሄጄ የ35 ዓመት ሙሉ ደንዳና ወጣት ሆኜ ተመለስኩ….››
‹‹አሀ ዲያስፖራ ነሀ….?››
‹‹አይ ዲያስፖራ ..!!! ‹ጽድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ ›ትላለች እናቴ… ለማንኛውም እወነቱን ንገረኝ ካልሺኝ … በእነዛ ዓመታት ውስጥ በሰው ሀገር ላይ ስዳክር ..ሞራሌን ከማንቆሻቆሽ…ሰው ሆኜ መፈጠሬን ከመጠየፍ እና ወጣትነቴ ላይ ጢቢ ጢቢ ከመጫወት ውጭ ምንም ያተረፍኩት ነገር አልነበረም…ብዙ ህልም በልቤ ብዙ ምኞት በውስጤ አጭቄ ነበር የተጓዘኩት …እርባነቢስ ሆኜ ባዶ እጄን በሀገሬ ለመሞት ብቻ ብዬ ነበር የተመለስኩት …ይገርማል አይደል?
ሰው እንዴት ለመሞት ብሎ ከደብቡ አፍሪካ ድረስ ኪሎሜትሮችን አቆርጦ ይመጣል ትይኝ ይሆናል..….?ለእኔ ግን ትርጉም ነበረው..››
‹‹ንገረኝ እስኪ ትርጉሙን…››ከሳዕታት ትርኪ ሚርኪ ወሬ እና መዛለል በኃላ ድንገት ምርር ወዳለ የህይወት ታሪክ ሀተታ መግባቱ አስደምሟታል አስደስቷታልም…አሁን እየነገራት ያለውን ታሪክ እሱ ሳይነግራት እንደተለመደው ወጭ እየጠበቀት ያለውን ንስሯን እንዲረዳት አድርጋ በዝርዝር ማወቅ ትችላለች..ግን አልፈለገችም …እንዲሁ እየጓጓችና ቀጥሎ ምን እንደሚናገር እየገመተች ቀጥታ ከራሱ አንደበት መስማቱ የሆነ የተለየ ስሜት ስለፈጠረባት ደስ ብሏታል…
ቀጠለ ‹‹በህይወቴ እያለሁ የመኖር ምኞቴ ሰልበው በድን አድርገውኝ …ወጣትነቴን ከንቱ አስቀርተውብኝ የመጨረሻውን ክስረት ማክሰራቸው ሳይበቃቸው …ከሞቴም በኃላ ክብር ስጋዬን ለሀገራቸው ምድር ልገብር …?አላደርገውም ፡፡ለዘላለም የባዕድ ሀገር አፈር ሆኜ መቅረት አልፈለኩም ..ይህ መልካም አይደለም…ቢያንስ አገሬ እትብቴን በክብር በወርቃማ አፈሯ ውስጥ ቀብራ ከማንነቷ ጋር እንዳወሀደችው ሁሉ ስሞትም በድኔን በክብር ልትቀበለኝ እና ለዘላለም በጉያዋ ልትሸሽገኝ ይገባል..አዎ እንደዛ ነው መሆን ያለበት..በዛ ላይ እናቴን ለመጨረሻ ጊዜ ማየት እፈልጋለሁ… አያየኋት መሰናበት፤ስሮ በመኖር እና እሷን መጦር ችዬ ላስደስታት ባልታደልም… እጇ ላይ ሞቼ አልቅሳ ልትቀብረኝ እና እርሟን ለማውጣት እንድትችል ግን እድሉን ላመቻችላት ይገባል..አዎ ስመጣ እንደዛ ብዬ እና እንደዛ ወስኜ ነበር …
‹‹ከዛስ….?››
‹‹ከደረስኩ ኋላማ … ቆይ ዛሬ ስል …ቆይ ትንሽ ልሰንብት ስል ..የመኖር ጉጉቴ ቀስ በቀስ ከሞተበት እያንሰራራ እና እየተቀሰቀሰ መጣ..ምንም አግኝቼ አልነበረም ..ከእናቴ የማገኘው ተንሰፍሳፊ ፍቅር እና ከጓደኞቼ የማገኘው ማፃናኛ …››
‹‹በጣም አሪፍ ታሪክ ነው ያለህ››
‹‹አዎ መራር የህይወት ገጠመኞች ለሰሚው ወይም ለፅሀፊው ሳቢ ታሪክ ይወጣቸዋል…››
‹‹ከዛስ እንዴት ሀሳብህምን ሙሉ በሙሉ ልትቀይር ቻልክ….?››
‹‹አሁንም ሙሉ በሙሉ አልተውኩትም…አሁንም የመሞት እቅዴ በውስጤ አለ…››
‹‹እሺ እንዴት ልታራዝመው ቻልክ….?››ጥያቄውን አስተካከለችለት፡፡
‹‹እንዴት መሰለሽ….ከዛ ከሰው ሀገር በገንዘብም በመንፈስም ክስርስር ብዬ የመጣሁ ቢሆንም ብዙም ሳልቆይ ሚስኪን የልጅነት ጓደኞቼ አዋጥተው አሁን የምጠቀምባትን ላዳ ገዝተው ሰጡኝ..በቃ የመሞት ሀሳቤን አራዘምኩት ..ለራሴ ሁለተኛ እድል ሰጠሁት..ቢያንስ ለጊዜው ሰርቼ ስጋዬን የማኖርበትን ካገኘሁ አንድ ቀን ምን አልባት ሁለተኛውን የህይወት ምኞቴን በሆነ ተአምር ሊሳካልኝ ይችል ይሆናል…ብዬ ተስፋ አደረኩና መጨረሻውን እስከማይ ሁለት ዓመት ተኩል በሀገሬ ኖርኩ..ዘና ብዬ ለማንም ለምንም ሳልጨነቅ…ባሳኘኝ ሰዓት እየሰራሁ ሲያሰኘኝ ደግሞ እየተኛው..የእናቴን ሽሮ እየበላሁ ተስፋዬን በመጠበቅ እንሆ አለሁልሽ››
‹‹ምንድነው ተስፋህ..ማለቴ ይሳከልኛል ብለህ የምትጠብቀው….?››
‹‹የልጅነት ፍቅሬን… ..አንድ ቀን ቀና ብላ ታየኛለች የሚል ተስፋ..አንድ ቀን ከቄስ ትምህርት ቤት ጀምሮ እንደማፋቅራት እና ዕድሜዬን ሙሉ በልቤ ተሸክሜያት ስዞር እንደኖርኩ ተረድታ በእቅፎ ታስገባኛለች ብዬ ተስፋ በማድረግ..አንድ ቀን እጄ ትገባለች በሚል ተስፋ…..››
‹‹ወየው ጉዴ!!›አለኝች በውስጧ፡ በዚህ ቅርብ ጊዜ ውስጥ የምትቀርባቸውና የምትመኛቸው ወንዶች ሁሉ እንዴት እንዴት ሆኖና ምንስ በሚሉት አጋጣሚ እንደዚህ በፍቅር ስክር ያሉና የታወሩ ሆነው እንደሚገኙ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም...?‹‹ይሄኛውንስ ዛሬ አልምረውም…በፍጽም፡፡››ስትል ፎከረችው፡፡
‹‹ይቅርታ ሙሉ ታሪኩን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ….››
‹‹እየነገርኩሽ እኮ ነው …እየተረተርኩልሽ…..ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል አይደል የሚባለው››
‹‹አይ እዚህ አይደለም…እኔ ቤት እንሂድና ተረጋግተን እየጠጣን ታወራልኛለህ….አሁን ሆቴሉም ሊዘጋ መሰለኝ››
‹‹ይቻላል››ይከራከረኛል ወይም ይቃወመኛል ብላ ነበር የጠበቀችው ..ቀድሟት ተነሳ ..ሂሳብ ከፍላ ተከተለችው …. እየተወለጋገድና እርስ በርስ እየተደጋገፉ ላደው ድረስ ሄድ ..ሹፌሩ ተቀብሏቸው እቤት ድረስ አደረሳቸውና የለሊቱን ግዳጅ ጨረሶ ተለያቸው..
እሷም ዛሬ ለዛውም ከመሸ ያወቀችውን ባለ ላዳ ይዛው ወደቤቷ ገባች…..
✨ይቀጥላል✨
#YouTube ቻናሌን አ.ረ.ረ..ረ!!!subscribe እያደረጋቹ😔
👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ቻናሉንም ይቀላቀሉ ለሌላም ያጋሩ👇
https://tttttt.me/atronosee
Follow my channel on WhatsApp 👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029VaDdoKaJENxsTyh8E43Z
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
‹‹ለማንኛውም ልድገምልሽ ኤርምያስ እባላለሁ…ለ15 ዓመት ያህል በማንዴላ ሀገር በሆነችው ደቡቡ አፍሪካ ጀሆንስበርግ ኖሬያለሁ… ወደሀገሬ ከተመለስኩ ሁለት ዓመት ከግማሽ ሆኖኛል፡፡የ20ዓመት አፍላ ፍንዳታ ሆኜ ሄጄ የ35 ዓመት ሙሉ ደንዳና ወጣት ሆኜ ተመለስኩ….››
‹‹አሀ ዲያስፖራ ነሀ….?››
‹‹አይ ዲያስፖራ ..!!! ‹ጽድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ ›ትላለች እናቴ… ለማንኛውም እወነቱን ንገረኝ ካልሺኝ … በእነዛ ዓመታት ውስጥ በሰው ሀገር ላይ ስዳክር ..ሞራሌን ከማንቆሻቆሽ…ሰው ሆኜ መፈጠሬን ከመጠየፍ እና ወጣትነቴ ላይ ጢቢ ጢቢ ከመጫወት ውጭ ምንም ያተረፍኩት ነገር አልነበረም…ብዙ ህልም በልቤ ብዙ ምኞት በውስጤ አጭቄ ነበር የተጓዘኩት …እርባነቢስ ሆኜ ባዶ እጄን በሀገሬ ለመሞት ብቻ ብዬ ነበር የተመለስኩት …ይገርማል አይደል?
ሰው እንዴት ለመሞት ብሎ ከደብቡ አፍሪካ ድረስ ኪሎሜትሮችን አቆርጦ ይመጣል ትይኝ ይሆናል..….?ለእኔ ግን ትርጉም ነበረው..››
‹‹ንገረኝ እስኪ ትርጉሙን…››ከሳዕታት ትርኪ ሚርኪ ወሬ እና መዛለል በኃላ ድንገት ምርር ወዳለ የህይወት ታሪክ ሀተታ መግባቱ አስደምሟታል አስደስቷታልም…አሁን እየነገራት ያለውን ታሪክ እሱ ሳይነግራት እንደተለመደው ወጭ እየጠበቀት ያለውን ንስሯን እንዲረዳት አድርጋ በዝርዝር ማወቅ ትችላለች..ግን አልፈለገችም …እንዲሁ እየጓጓችና ቀጥሎ ምን እንደሚናገር እየገመተች ቀጥታ ከራሱ አንደበት መስማቱ የሆነ የተለየ ስሜት ስለፈጠረባት ደስ ብሏታል…
ቀጠለ ‹‹በህይወቴ እያለሁ የመኖር ምኞቴ ሰልበው በድን አድርገውኝ …ወጣትነቴን ከንቱ አስቀርተውብኝ የመጨረሻውን ክስረት ማክሰራቸው ሳይበቃቸው …ከሞቴም በኃላ ክብር ስጋዬን ለሀገራቸው ምድር ልገብር …?አላደርገውም ፡፡ለዘላለም የባዕድ ሀገር አፈር ሆኜ መቅረት አልፈለኩም ..ይህ መልካም አይደለም…ቢያንስ አገሬ እትብቴን በክብር በወርቃማ አፈሯ ውስጥ ቀብራ ከማንነቷ ጋር እንዳወሀደችው ሁሉ ስሞትም በድኔን በክብር ልትቀበለኝ እና ለዘላለም በጉያዋ ልትሸሽገኝ ይገባል..አዎ እንደዛ ነው መሆን ያለበት..በዛ ላይ እናቴን ለመጨረሻ ጊዜ ማየት እፈልጋለሁ… አያየኋት መሰናበት፤ስሮ በመኖር እና እሷን መጦር ችዬ ላስደስታት ባልታደልም… እጇ ላይ ሞቼ አልቅሳ ልትቀብረኝ እና እርሟን ለማውጣት እንድትችል ግን እድሉን ላመቻችላት ይገባል..አዎ ስመጣ እንደዛ ብዬ እና እንደዛ ወስኜ ነበር …
‹‹ከዛስ….?››
‹‹ከደረስኩ ኋላማ … ቆይ ዛሬ ስል …ቆይ ትንሽ ልሰንብት ስል ..የመኖር ጉጉቴ ቀስ በቀስ ከሞተበት እያንሰራራ እና እየተቀሰቀሰ መጣ..ምንም አግኝቼ አልነበረም ..ከእናቴ የማገኘው ተንሰፍሳፊ ፍቅር እና ከጓደኞቼ የማገኘው ማፃናኛ …››
‹‹በጣም አሪፍ ታሪክ ነው ያለህ››
‹‹አዎ መራር የህይወት ገጠመኞች ለሰሚው ወይም ለፅሀፊው ሳቢ ታሪክ ይወጣቸዋል…››
‹‹ከዛስ እንዴት ሀሳብህምን ሙሉ በሙሉ ልትቀይር ቻልክ….?››
‹‹አሁንም ሙሉ በሙሉ አልተውኩትም…አሁንም የመሞት እቅዴ በውስጤ አለ…››
‹‹እሺ እንዴት ልታራዝመው ቻልክ….?››ጥያቄውን አስተካከለችለት፡፡
‹‹እንዴት መሰለሽ….ከዛ ከሰው ሀገር በገንዘብም በመንፈስም ክስርስር ብዬ የመጣሁ ቢሆንም ብዙም ሳልቆይ ሚስኪን የልጅነት ጓደኞቼ አዋጥተው አሁን የምጠቀምባትን ላዳ ገዝተው ሰጡኝ..በቃ የመሞት ሀሳቤን አራዘምኩት ..ለራሴ ሁለተኛ እድል ሰጠሁት..ቢያንስ ለጊዜው ሰርቼ ስጋዬን የማኖርበትን ካገኘሁ አንድ ቀን ምን አልባት ሁለተኛውን የህይወት ምኞቴን በሆነ ተአምር ሊሳካልኝ ይችል ይሆናል…ብዬ ተስፋ አደረኩና መጨረሻውን እስከማይ ሁለት ዓመት ተኩል በሀገሬ ኖርኩ..ዘና ብዬ ለማንም ለምንም ሳልጨነቅ…ባሳኘኝ ሰዓት እየሰራሁ ሲያሰኘኝ ደግሞ እየተኛው..የእናቴን ሽሮ እየበላሁ ተስፋዬን በመጠበቅ እንሆ አለሁልሽ››
‹‹ምንድነው ተስፋህ..ማለቴ ይሳከልኛል ብለህ የምትጠብቀው….?››
‹‹የልጅነት ፍቅሬን… ..አንድ ቀን ቀና ብላ ታየኛለች የሚል ተስፋ..አንድ ቀን ከቄስ ትምህርት ቤት ጀምሮ እንደማፋቅራት እና ዕድሜዬን ሙሉ በልቤ ተሸክሜያት ስዞር እንደኖርኩ ተረድታ በእቅፎ ታስገባኛለች ብዬ ተስፋ በማድረግ..አንድ ቀን እጄ ትገባለች በሚል ተስፋ…..››
‹‹ወየው ጉዴ!!›አለኝች በውስጧ፡ በዚህ ቅርብ ጊዜ ውስጥ የምትቀርባቸውና የምትመኛቸው ወንዶች ሁሉ እንዴት እንዴት ሆኖና ምንስ በሚሉት አጋጣሚ እንደዚህ በፍቅር ስክር ያሉና የታወሩ ሆነው እንደሚገኙ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም...?‹‹ይሄኛውንስ ዛሬ አልምረውም…በፍጽም፡፡››ስትል ፎከረችው፡፡
‹‹ይቅርታ ሙሉ ታሪኩን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ….››
‹‹እየነገርኩሽ እኮ ነው …እየተረተርኩልሽ…..ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል አይደል የሚባለው››
‹‹አይ እዚህ አይደለም…እኔ ቤት እንሂድና ተረጋግተን እየጠጣን ታወራልኛለህ….አሁን ሆቴሉም ሊዘጋ መሰለኝ››
‹‹ይቻላል››ይከራከረኛል ወይም ይቃወመኛል ብላ ነበር የጠበቀችው ..ቀድሟት ተነሳ ..ሂሳብ ከፍላ ተከተለችው …. እየተወለጋገድና እርስ በርስ እየተደጋገፉ ላደው ድረስ ሄድ ..ሹፌሩ ተቀብሏቸው እቤት ድረስ አደረሳቸውና የለሊቱን ግዳጅ ጨረሶ ተለያቸው..
እሷም ዛሬ ለዛውም ከመሸ ያወቀችውን ባለ ላዳ ይዛው ወደቤቷ ገባች…..
✨ይቀጥላል✨
#YouTube ቻናሌን አ.ረ.ረ..ረ!!!subscribe እያደረጋቹ😔
👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ቻናሉንም ይቀላቀሉ ለሌላም ያጋሩ👇
https://tttttt.me/atronosee
Follow my channel on WhatsApp 👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029VaDdoKaJENxsTyh8E43Z
👍121❤11🤔7🔥3😁2👏1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
መኝታ ቤቷ ገብታ ልብሷን ከቀያየረች በኋላ የጀመሩትን አይነት መጠጥ አምጥታ ለሁለቱም ቀዳችና ወደጫወታቸውን እዲመለሱ ተመቻቸች..
‹‹እሺ አሁን ካቆምክበት ጀምርልኝ››
‹‹ምን….? ››አለት ሁሉን ነገር የረሳው ይመስላል
‹‹ታሪክህን እየነገርከኝ ነበር››
‹‹እ..አዎ…ግን የት ላይ ነበር ያቆምኩት….?››
‹‹ስለፍቅረኛህ ጀምረህልኝ ነበር..በህይወት የምትኖርበት ምክንያት እሷን አንድ ቀን አገኛት ይሆናል በሚል ጉጉት ምክንያት እንደሆነ ነግረኸኝ ነበር ያቆምከው››
‹‹አዎ….አይገርምሽም …
እስከጥቂት ቀናት ድረስ እኮ ምንም አይነት ተስፋ አልነበረኝም…››
‹‹ቆይ ጠይቀሀት እንቢ ብላህ ነው….?››
‹‹አረ መጠየቅ…ትቀልጂያለሽ እንዴ ….?ቀና ብዬ እንኳን ሰላምታ ልሰጣት ድፍረቱ የለኝም.››
‹‹ግን እኮ እንደዛ አይነት ሰው አትመስልም..በጣም ደፋር ግልጽ እና በራስ መተማመን ያለህ ሰው ነህ››አለችው ከልቧ..
‹‹እኔም እንደዛ ነኝ ብዬ አምናለሁ..ፍቅር የሚባለው ነገር ግን ዋና ባህሪው ያልሆንሺውን ሆነሽ እንድትገኚ ማድረግ ይመስለኛል…እጅግ ክፉ የነበርሽው ሰው በፍቅር ውስጥ ስትሆኚ ስጋዬን ግፈፉት እስከማለት ድርስ የሚደርስ ደግነት ያጓናጽፍሻል….ደንዳናና ኮስታራ የነበርሽው፤አልቃሽና ተርበትባች ሆነሽ ቁጭ….ፍቅር እንደዛ አይነት በሽታ ነው፡፡››
‹‹ቢሆንም ….ይህን ያህል ካፈቀርካት የሆነ ነገር ማድረግ ነበረብህ ..ለመሆኑ የት ነው የምትኖረው….?››
‹‹የሚገርመው እሱ ነው..በእሷ ቤት እና በእኔ ቤት መካከል ያለሁ እርቀት ግማሽ ኪሎ ሜትር አይሆንም…. ሁለታችንም ሳሪስ በአንድ ሰፍር ተወልደን እዛው አንድ ሰፈር ያደግን ነን…ቤተሰቦቻን የአንድ እድር አባል ሆነው፤አንድ የጽዋ ማህበር መስርተው ዕድሜያቸውን በጉርብትና የኖሩ ናቸው….አንድ ቄስ ትምህር ቤትፊደል መቁጠር ጀምረን .አብረን ኤለመንተር የገባን የእድሜ እኩዬች ነን››
‹‹ይገርማል!!››
‹‹እውነትሽን ነው በጣም ይገርማል…. ከ1ኛ ክፍል አንስቶ እስከ አስረኛ ክፍል አብረን ነበር የተማርነው…በተለይ ዘጠነኛ ክፍል አንድ ወንበር ላይ ነበር የምንቀመጠው…ግን በወቅቱ እኔ ግማሽ ልቤ ነበር ክፍል ውስጥ የሚገኘው… እሷ ደግሞ አካሏም ነፍሶም ትምርቱ ላይ የተጣበቀ ነበር፡፡ግን የሚያመሳስለን አንድ ነገር ቢኖር ሁለታችንም ተአምር ካልተፈጠረ በስተቀር ከትምህርት ቤት አንቀርም ነበር..››
‹‹ለምን ….?››አለችው ገለጻው ገርሞት
‹‹እሷ ለትምህርት ባላት ፍቅር የተነሳ እኔ ደግሞ ለእሷ ካለኝ ፍቅር የተነሳ….››
አሳቃት….ብርጭቆውን አንስቶ ከተጎነጨለት በኃላ ቀጠለ
‹‹እሷ እንደማንኛውም የክፍል ጓደኛ ግን ደግሞ ከዛም ትንሽ ከፍ ባለ የሰፈር ልጅነት እና አብሮ አደግነት ነው የምትቀርበኝ…እኔ ደግሞ በዚህ አለም ላይ ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው ያሉኝ.. እናቴ እና እሷ ብቻ..በቃ..ያኔ አብሬት በምማርበት በዛ ጊዜ ብቻ አልነበረም እንደዛ የሚሰማኝ.. አገር ለቅቄ በስደትም እያለው እንደዛ ነበር እምነቴ…የሆነች ሴት በሆነ ነገሮቾ ትንሽም እንኳን ከእሷ ጋር ካልተመሳሰለችልኝ..የሆነ የእሷን ነገር እንዳስታውስ ካላደረገችኝ አንድ ደቂቃም ላወራት ወይም አጠገቧ ልቀመጥ አይቻለኝም….ከአስር አመት መለያየት በኃላ ከ10 ዓመት ናፍቆት በኃላ እሷን እና እናቴን አንዴ አይቼ ለመሞት ወስኜ ወደሀገሩ ስመጣ…እሷን በተመለከተ ጭራሽ ተስፋ የሚያስቋርጥ ነገር ነው ያጋጠመኝ…፡፡አፍላ ልጃገረድ ገና አጎጠጎጤ ሆና ጥያት የሄድኳት ልጅ አድጋና ፈክታ ሙሉ ሴት ሆና ጠበቀችኝ…፡፡የ10ኛ ክፍል ተማሪ ሆና የተለየኋት ልጅ ዶክተር ተብላ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ ትልቅ ባለሞያ ሆና አገኘኋት..እና የሩቅ ህልሜ የነበረችው ልጅ ጭራሽ መቼም የማትፈታ ቅዠቴ እንደሆነች አሰብኩ…ሳያት በሩቅ መሸሽ ጀመርኩ፡፡ድንገት መንገድ ላይ ስንገጣጠም እንኳን ቅንድቤን ከፍ ዝቅ በማድረግ አንገቴን አቀርቅሬ ሰላምታ ለመስጠት ከመሞከር ውጭ እሷ እንኳን ለሰላምታዬ አፀፋውን መመለሷ እና አለመመለሷን እርግጠኛ ሆኜ አላውቅም፡፡ይህቺ ልጅ የእኔ ልጅነቴ ነች….የሩቅ እሩቅ ትዝታዬ …ብዙ ብዙ ለሊቶች በህልሜ ያየኋት… ብዙ ብዙ ታሪክ ያጫወተችኝ….ብዙ ብዙ ነገር ያወጋኋት…ያወጋችኝ..፡፡እንደዛ ብቻ ሳይሆን ደጋግሜ ያገባኋት…ብዙ ብዙ ልጆች የወለደችልኝ…ብዙ የሳምኳት፤ ብዙ የሳመችኝ…ብዙ ያፈቀርኳት፤ብዙ የወደደቺኝ…ግን ሁሉም በህልሜ የሆነ ነበር …››
‹‹ምን አይነት ፍቅር ነው..ስል አሰብኩ ደግሞ ከዚህች ልጅ ጋር የሚያመሳስለኝ አንድ ነገር ይኖር ይሁን .. ….?አዎ መኖርማ አለበት ….እደዛ ቢሆን ነው ይሄን ሁሉ ሰዓት አብሮኝ ያሳለፈው…እቤቴ ድረስ ተከትሎኝ በለሊት የመጣው…አዎ እንደዛ ቢሆን ነው ሚስጥሩን ዘክዝኮ የሚነግረኝ…››ስትል የራሷን ግምት ወሰደች…ግምቷ እውነት ሆኖ እስከአልጋ መዋደቅና መዋሰብ ድረስ ያደርሷቸው እንደሆነ አሁንም በውስጧ እያሳላሳላች ነው ፡
ቀጠለ እሱ…‹‹እና ይገርምሻል ከሶስት ቀን በፊት ያልጠበቅኩት አጋጣሚ ተከሰተ…››
‹‹ምን ተከሰተ….?››
‹‹ወደሀገሬ ከተመለስኩ ከሁለት ዓመት ተኩል በኃላ ትናንት….ድብር እና ጭፍግግ ብሎኝ ሰፈር ላዳዬ አቁሜ እኔም ላዳዬ ውስጥ ወንበሬን ወደኃላ ለጥጬ መፅሀፍ በማንበብ በተመስጦ ላይ እያለሁ...በሀይለኛው የላዳው የኃላዋ በራፍ ሲንኳኳ የሆነ የእብድ ድርጊት መስሎኝ በርግጌ ተነሳሁና አንገቴን በመስኮት አስግጌ ወደ ኃላው ተመለከተኩ…
‹‹እንዴ ሰላም…!!!!!››
‹‹ክፈትልኝ››
‹‹እሺ ››ተረብትብቼ ከፈትኩላት..ተስፈንጥራ ገባች…የሆነ ሰው ከኃላ እያባረራት ይመስላል..ፀጉሯ ሁሉ ጭብርር ብሏል…የአይኖቾ ደም መልበስ ምን አልባት ለቀናት ስታለቅስ እንደቆየች ምስክር ናቸው…..አለባበሶም እንደነገሩ እና ያልታሰበበት ነው….››የአመታት ህልሜ የሆነች ልጅ በእንዲህ አይነት ያልታሰበበት አጋጣሚ ላዳዬ ውስጥ ትገባለች ብዬ እንኳን ማሰብ አልሜ እንኳን አላውቅም…..
‹‹ንዳው ››አለችኝ
ህልም ውስጥ ያለሁ ነበር የመሰለኝ ፡፡ ትዛዞን ተቀብዬ …ሞተሬን አንቀሳቀስኩ እና ነደሁት
‹‹-የትኛው ፖሊስ ጣቢያ እንሂድ….?››ጠየቅኳት
‹‹የምን ፖሊስ ጣቢያ….?›› አለችን ግራ በመጋባት
-‹‹አይ እንዲሁ ነገር ስራሽን ስገመግመው የሆንሽው ነገር ያለ ስለመሰለኝ ነው..››
‹‹ሆኜያለሁ...አዎ የሆነ ነገር ሆኜያለሁ… መች አልሆንኩም አልኩህ …ግን ወደ ፖሊስ ጣቢያ መሄድ ምን ይፈይድልኛል..….?››አለቺኝ.‹‹ይቅርታ እሺ የት ልወስድሽ..….?››አልኳት
በመለማመጥ..እወነቴን ነው በዛች ላዳ ጆሀንስበርግ አድርሰኝ ብትለኝ እንኳን እድሜ ልክ ይውሰድብኝ እንጂ እንቢ አልላትም…በምን አቅሜ…በእሷ መታዘዝ እኮ ለእኔ እድል ነው…የአለምን ህዝብ አጥፋልኝ ብትለኝ እንኳን ባልችልም ከመሞከር ወደኃላ አልልም፡፡
‹‹እኔ እንጃ የሆነ ሰው እንደእኔ ሲሆን የት ነው የሚሄደው..….?ወይም የት ነው መሄድ ያለበት..››በቀላሉ ልመልሰው የማልችለውን ውስብስብና ግራአጋቢ ጥያቄ ጠየቀችኝ ‹‹እኔ እንጃ ምን አልባት ቤተክሪስትያን ልውሰድሽ….?››ይሻል የመሰለኝን አማራጭ አቀረብኩላት ፡
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
መኝታ ቤቷ ገብታ ልብሷን ከቀያየረች በኋላ የጀመሩትን አይነት መጠጥ አምጥታ ለሁለቱም ቀዳችና ወደጫወታቸውን እዲመለሱ ተመቻቸች..
‹‹እሺ አሁን ካቆምክበት ጀምርልኝ››
‹‹ምን….? ››አለት ሁሉን ነገር የረሳው ይመስላል
‹‹ታሪክህን እየነገርከኝ ነበር››
‹‹እ..አዎ…ግን የት ላይ ነበር ያቆምኩት….?››
‹‹ስለፍቅረኛህ ጀምረህልኝ ነበር..በህይወት የምትኖርበት ምክንያት እሷን አንድ ቀን አገኛት ይሆናል በሚል ጉጉት ምክንያት እንደሆነ ነግረኸኝ ነበር ያቆምከው››
‹‹አዎ….አይገርምሽም …
እስከጥቂት ቀናት ድረስ እኮ ምንም አይነት ተስፋ አልነበረኝም…››
‹‹ቆይ ጠይቀሀት እንቢ ብላህ ነው….?››
‹‹አረ መጠየቅ…ትቀልጂያለሽ እንዴ ….?ቀና ብዬ እንኳን ሰላምታ ልሰጣት ድፍረቱ የለኝም.››
‹‹ግን እኮ እንደዛ አይነት ሰው አትመስልም..በጣም ደፋር ግልጽ እና በራስ መተማመን ያለህ ሰው ነህ››አለችው ከልቧ..
‹‹እኔም እንደዛ ነኝ ብዬ አምናለሁ..ፍቅር የሚባለው ነገር ግን ዋና ባህሪው ያልሆንሺውን ሆነሽ እንድትገኚ ማድረግ ይመስለኛል…እጅግ ክፉ የነበርሽው ሰው በፍቅር ውስጥ ስትሆኚ ስጋዬን ግፈፉት እስከማለት ድርስ የሚደርስ ደግነት ያጓናጽፍሻል….ደንዳናና ኮስታራ የነበርሽው፤አልቃሽና ተርበትባች ሆነሽ ቁጭ….ፍቅር እንደዛ አይነት በሽታ ነው፡፡››
‹‹ቢሆንም ….ይህን ያህል ካፈቀርካት የሆነ ነገር ማድረግ ነበረብህ ..ለመሆኑ የት ነው የምትኖረው….?››
‹‹የሚገርመው እሱ ነው..በእሷ ቤት እና በእኔ ቤት መካከል ያለሁ እርቀት ግማሽ ኪሎ ሜትር አይሆንም…. ሁለታችንም ሳሪስ በአንድ ሰፍር ተወልደን እዛው አንድ ሰፈር ያደግን ነን…ቤተሰቦቻን የአንድ እድር አባል ሆነው፤አንድ የጽዋ ማህበር መስርተው ዕድሜያቸውን በጉርብትና የኖሩ ናቸው….አንድ ቄስ ትምህር ቤትፊደል መቁጠር ጀምረን .አብረን ኤለመንተር የገባን የእድሜ እኩዬች ነን››
‹‹ይገርማል!!››
‹‹እውነትሽን ነው በጣም ይገርማል…. ከ1ኛ ክፍል አንስቶ እስከ አስረኛ ክፍል አብረን ነበር የተማርነው…በተለይ ዘጠነኛ ክፍል አንድ ወንበር ላይ ነበር የምንቀመጠው…ግን በወቅቱ እኔ ግማሽ ልቤ ነበር ክፍል ውስጥ የሚገኘው… እሷ ደግሞ አካሏም ነፍሶም ትምርቱ ላይ የተጣበቀ ነበር፡፡ግን የሚያመሳስለን አንድ ነገር ቢኖር ሁለታችንም ተአምር ካልተፈጠረ በስተቀር ከትምህርት ቤት አንቀርም ነበር..››
‹‹ለምን ….?››አለችው ገለጻው ገርሞት
‹‹እሷ ለትምህርት ባላት ፍቅር የተነሳ እኔ ደግሞ ለእሷ ካለኝ ፍቅር የተነሳ….››
አሳቃት….ብርጭቆውን አንስቶ ከተጎነጨለት በኃላ ቀጠለ
‹‹እሷ እንደማንኛውም የክፍል ጓደኛ ግን ደግሞ ከዛም ትንሽ ከፍ ባለ የሰፈር ልጅነት እና አብሮ አደግነት ነው የምትቀርበኝ…እኔ ደግሞ በዚህ አለም ላይ ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው ያሉኝ.. እናቴ እና እሷ ብቻ..በቃ..ያኔ አብሬት በምማርበት በዛ ጊዜ ብቻ አልነበረም እንደዛ የሚሰማኝ.. አገር ለቅቄ በስደትም እያለው እንደዛ ነበር እምነቴ…የሆነች ሴት በሆነ ነገሮቾ ትንሽም እንኳን ከእሷ ጋር ካልተመሳሰለችልኝ..የሆነ የእሷን ነገር እንዳስታውስ ካላደረገችኝ አንድ ደቂቃም ላወራት ወይም አጠገቧ ልቀመጥ አይቻለኝም….ከአስር አመት መለያየት በኃላ ከ10 ዓመት ናፍቆት በኃላ እሷን እና እናቴን አንዴ አይቼ ለመሞት ወስኜ ወደሀገሩ ስመጣ…እሷን በተመለከተ ጭራሽ ተስፋ የሚያስቋርጥ ነገር ነው ያጋጠመኝ…፡፡አፍላ ልጃገረድ ገና አጎጠጎጤ ሆና ጥያት የሄድኳት ልጅ አድጋና ፈክታ ሙሉ ሴት ሆና ጠበቀችኝ…፡፡የ10ኛ ክፍል ተማሪ ሆና የተለየኋት ልጅ ዶክተር ተብላ ትልቅ ሆስፒታል ውስጥ ትልቅ ባለሞያ ሆና አገኘኋት..እና የሩቅ ህልሜ የነበረችው ልጅ ጭራሽ መቼም የማትፈታ ቅዠቴ እንደሆነች አሰብኩ…ሳያት በሩቅ መሸሽ ጀመርኩ፡፡ድንገት መንገድ ላይ ስንገጣጠም እንኳን ቅንድቤን ከፍ ዝቅ በማድረግ አንገቴን አቀርቅሬ ሰላምታ ለመስጠት ከመሞከር ውጭ እሷ እንኳን ለሰላምታዬ አፀፋውን መመለሷ እና አለመመለሷን እርግጠኛ ሆኜ አላውቅም፡፡ይህቺ ልጅ የእኔ ልጅነቴ ነች….የሩቅ እሩቅ ትዝታዬ …ብዙ ብዙ ለሊቶች በህልሜ ያየኋት… ብዙ ብዙ ታሪክ ያጫወተችኝ….ብዙ ብዙ ነገር ያወጋኋት…ያወጋችኝ..፡፡እንደዛ ብቻ ሳይሆን ደጋግሜ ያገባኋት…ብዙ ብዙ ልጆች የወለደችልኝ…ብዙ የሳምኳት፤ ብዙ የሳመችኝ…ብዙ ያፈቀርኳት፤ብዙ የወደደቺኝ…ግን ሁሉም በህልሜ የሆነ ነበር …››
‹‹ምን አይነት ፍቅር ነው..ስል አሰብኩ ደግሞ ከዚህች ልጅ ጋር የሚያመሳስለኝ አንድ ነገር ይኖር ይሁን .. ….?አዎ መኖርማ አለበት ….እደዛ ቢሆን ነው ይሄን ሁሉ ሰዓት አብሮኝ ያሳለፈው…እቤቴ ድረስ ተከትሎኝ በለሊት የመጣው…አዎ እንደዛ ቢሆን ነው ሚስጥሩን ዘክዝኮ የሚነግረኝ…››ስትል የራሷን ግምት ወሰደች…ግምቷ እውነት ሆኖ እስከአልጋ መዋደቅና መዋሰብ ድረስ ያደርሷቸው እንደሆነ አሁንም በውስጧ እያሳላሳላች ነው ፡
ቀጠለ እሱ…‹‹እና ይገርምሻል ከሶስት ቀን በፊት ያልጠበቅኩት አጋጣሚ ተከሰተ…››
‹‹ምን ተከሰተ….?››
‹‹ወደሀገሬ ከተመለስኩ ከሁለት ዓመት ተኩል በኃላ ትናንት….ድብር እና ጭፍግግ ብሎኝ ሰፈር ላዳዬ አቁሜ እኔም ላዳዬ ውስጥ ወንበሬን ወደኃላ ለጥጬ መፅሀፍ በማንበብ በተመስጦ ላይ እያለሁ...በሀይለኛው የላዳው የኃላዋ በራፍ ሲንኳኳ የሆነ የእብድ ድርጊት መስሎኝ በርግጌ ተነሳሁና አንገቴን በመስኮት አስግጌ ወደ ኃላው ተመለከተኩ…
‹‹እንዴ ሰላም…!!!!!››
‹‹ክፈትልኝ››
‹‹እሺ ››ተረብትብቼ ከፈትኩላት..ተስፈንጥራ ገባች…የሆነ ሰው ከኃላ እያባረራት ይመስላል..ፀጉሯ ሁሉ ጭብርር ብሏል…የአይኖቾ ደም መልበስ ምን አልባት ለቀናት ስታለቅስ እንደቆየች ምስክር ናቸው…..አለባበሶም እንደነገሩ እና ያልታሰበበት ነው….››የአመታት ህልሜ የሆነች ልጅ በእንዲህ አይነት ያልታሰበበት አጋጣሚ ላዳዬ ውስጥ ትገባለች ብዬ እንኳን ማሰብ አልሜ እንኳን አላውቅም…..
‹‹ንዳው ››አለችኝ
ህልም ውስጥ ያለሁ ነበር የመሰለኝ ፡፡ ትዛዞን ተቀብዬ …ሞተሬን አንቀሳቀስኩ እና ነደሁት
‹‹-የትኛው ፖሊስ ጣቢያ እንሂድ….?››ጠየቅኳት
‹‹የምን ፖሊስ ጣቢያ….?›› አለችን ግራ በመጋባት
-‹‹አይ እንዲሁ ነገር ስራሽን ስገመግመው የሆንሽው ነገር ያለ ስለመሰለኝ ነው..››
‹‹ሆኜያለሁ...አዎ የሆነ ነገር ሆኜያለሁ… መች አልሆንኩም አልኩህ …ግን ወደ ፖሊስ ጣቢያ መሄድ ምን ይፈይድልኛል..….?››አለቺኝ.‹‹ይቅርታ እሺ የት ልወስድሽ..….?››አልኳት
በመለማመጥ..እወነቴን ነው በዛች ላዳ ጆሀንስበርግ አድርሰኝ ብትለኝ እንኳን እድሜ ልክ ይውሰድብኝ እንጂ እንቢ አልላትም…በምን አቅሜ…በእሷ መታዘዝ እኮ ለእኔ እድል ነው…የአለምን ህዝብ አጥፋልኝ ብትለኝ እንኳን ባልችልም ከመሞከር ወደኃላ አልልም፡፡
‹‹እኔ እንጃ የሆነ ሰው እንደእኔ ሲሆን የት ነው የሚሄደው..….?ወይም የት ነው መሄድ ያለበት..››በቀላሉ ልመልሰው የማልችለውን ውስብስብና ግራአጋቢ ጥያቄ ጠየቀችኝ ‹‹እኔ እንጃ ምን አልባት ቤተክሪስትያን ልውሰድሽ….?››ይሻል የመሰለኝን አማራጭ አቀረብኩላት ፡
👍85❤8😁2👏1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
የንስሯ ጭንቅላቷ ላይ ማረፍ ነበር ከእንቅልፏ ያባነናት….በመከራ አይኗን ገልጣ ዙሪያዋን ስትቃኝ እራሷን እዛው ቅድም የተዘረረችበት ወለል ላይ እርቃኗን አገኘችው….ባለ ላደውም የሞተ እስኪመስል ድረስ ትንፋሹ ጠፍቶ እግሮቾ መካከል ጭንቅላቱን ቀብሮ በተመሳሳይ እርቃኑን ተዘርሯል ….ቀስ ብላ ከላዮ ላይ ገልበጥ አደረገችውና እና እራሷን በማላቀቅ ሾልካ ወደ ሻወር በመሄድ ለ5 ደቅቃ ውሃ በላይዋ ላይ አፈሰሰችና..
ከዛ ወደመኝታ ቤቷ ተመልሳ ቢጃማ ለበሰችና ባለ ላዳውን እንደምንም እየጎተተችም እየደገፈችውም ወስዳ አልጋው ላይ በማስተኛት ብርድልብስ ካለበስችው በኋላ ወደሳሎን አመራች…..ንስሯም ተከተላት..፡፡
አዎ ሊነጋ መሆኑን ከውጭ የሚሰማውን የወፎች ዝማሬ በማዳመጥ ተረዳች …ሳሎኖ እንደደረሰች ተስተካክላ ከተቀመጠች በኋላ ንስሯ ያየውን እንዲያሳየት… ያወቀውን እንዲያሳውቃት አዕምሮዋን ከእሱ ጋ አቆራኘችው…
ሰላምና አባቷ…ፍቅራቸው ከአባትና ከልጅም የዘለል አይነት ነው..ኤርምያስ እንዳለው እናትም አባትም ወንድምም እህትም ሆነው ነው ያሳደጎት…ግን አሁን ስላለችበት ሁኔታ ብቻ ያለውን ታሪክ ከንስሯ በተረዳችው የሚከተለውን ነው
ቀጥታ ቤታቸው ገባች… መኝታ ቤት ወደመሰላት ክፍል ተጓዘች… አዎ ትክክል ነች ያልተነጠፈ እና የተዝረከረከ አልጋ … አልጋው ላይ የተዘረረች ውብ ለጋ ሀዘን የሰበራት ወጣት ተኝታለች…..ወለሉ ጠቅላላ በመጠጥ ጠርሙሶች እና በተበታተኑት ልብሶች ተሞልቷል..አንድ ግዙፍ አራት መአዘን ፍሪጅ አልጋውን ተደግፎ ይታያል…ትኩረቷን ወደፍሪጁ አመዘነበት… ውስጡን አየችው… .ህልም ውስጥ ነኝ እንዴ ያስብላል… …ነጭ ሱፍ ለብሶ ነጭ ሸሚዝና ቀይ ከረባት ያደረገ እንቅልፍ የተኛ የሚመስል ሰው ፍሪጅ ውስጥ ይታያል.. ..አባቷ ነው ….የሰላም አባት..አሁን የሆነ ነገር የገባት ነው..ልጅቷ እንደጠረጠረችውም አደጋ ላይ ነች…ሰላም አባቷን አጥታለች..ሰላም አባቷን መሬት ውስጥ ቀብራ ለዘላላም ለመለየት ድፍረቱንም ጭካኔውንም ለማግኘት አልቻለችም….
/////
ነገሩን በዝርዝር ለመረዳት አምስት ቀን ወደኃላ እንመለስ
እንደማንኛውም ቀን እየተጎራረሱ እራት በሉ…እያተሳሳቁ ዜናና ፊልም አዩ…አራት ሰዓት አካባቢ ወደመኝታቸው አመሩ….ሰላም አባቷን መኝታ ቤት አስገብታ እንዲተኙ ካደረገች በኃላ ግንባራቸውን ስማ ተሰናብታ ወደመኝታዋ ልትሄድ ስትል
‹‹ሰላሜ››ሲሉ ጠሯት
‹‹አቤት አባ›››
‹‹አብረሺኝ ተኚ››
ዘላ አልጋው ላይ ወጣችን ብድርብሱን ገልጣ ከውስጥ በመግባት እቅፋቸው ውስጥ ገባች…..ይህ አዲስ ነገር አይደለም..ተለያይተው ከሚተኙበት ይልቅ አንድ ላይ የሚተኙባቸው ቀናቶች የበዙ ነበሩ..ሁለቱም ትንሽ ሲከፋቸው ወይንም አመም ሲያደርጋቸው..ወይንም እንዲሁ ለብቻ መተኛት ሲደብራቸው ዛሬ እኔ ጋር ትተኚ..?ዛሬ አብረሀኝ ትተኛ..? እየተባባሉ አንድ ቀን እሷ ክፍል አንድ ቀን እሳቸው ክፍል ይተኛሉ..እና የተለመደ ነው፡፡
ችግሩ ንጊ ላይ ከእንቅልፏ ባና ከእቅፋቸው ስትወጣ ነበር የተፈጠረው….እጃቸውን ከሰውነቷ ላይ ሳታነሳ በተለየ ሁኔታ ቀዘቀዛት…..ቀስ ብለ ወጣችና አየቻቸው..ጸጥ ያለ ፊት ነበር..ዝም ያለ ፊት…እጇን ወደ አንገታቸው ላከች ….ትንፋሽ አልባ ሆነዋል..
‹‹አባዬ ..አባዬ›› ወዘወዘቻቸው…ጮኸች……..ወደመኝታ ቤቷ በሩጫ ሄደችና የልብ ማዳመጫ መሳሪዋን አመጣች…ምንም የለም..?…ጮኸች…ሁሉ ነገር ረፍዶ ነበር..ፀሀይ በጠለቀችበት ቀርታ ነበር…ጨረቃ በደመናው ሙሉ በሙሉ ተሸንፋ ከስማ ነበር…ምጽአት ደርሶ ነጋሪት እየተጎሰመ እና መለከት እየተነፋ ነበር…..
አባቷ እርግጥ ህመም ላይ ከነበሩ ወራት አልፏቸዋል….ግን እየተንከባከበቻቸው እና በትክክል የህክምና ክትትል እያደረገችላቸው ነበረ…ምንም የተለየ እና ለሞት የሚያሰጋ ምልክት አልተመለከተችም….የት ጋር ነው የተሸወደችው…..?ማወቅ አልቻለችም…፡፡ ለሳዕታት እሬሳውን ላይ ተኝታ ስትነፈርቅ ቆየች…ስልክ ደውላ ለወዳጆቾ ልትናገር ፈለገችና መደወል ከጀመረች በኃላ መልሳ ተወችው
‹‹አባቴን ልቀብር…..?አባቴንም ፈጽሞ አልቀብርም…….ለሳዕታት ካሰበች በኃላ ወሰነች‹‹..አብሬው እሞታለሁ..ግን ለመሞት እስክቆርጥ ድረስ እሱም አይቀበርም›› አለችና…ባላት የህክምና እውቀት በመጠቀም ሬሳው እንዳይበሰብስ አድርጋ በባለመስታወት ፍሪጅ ውስጥ በማድረግ መኝታ ቤት ውስጥ ሬሳውን ደብቃ አስቀመጠች….እና ይሄ ነው የሚያስጨንቃት…እና በዚህ ጊዜ ነበር ኤርምያስ ላዳ ውስጥ የገባችው….ይሄን ችግር ነበር እሱ ሊያውቅና ሊረዳላት ያልቻለው…..በዚህ ከቀጠለች በጥቂት ቀናት ውስጥ ወይ አዕምሮዋ ተነክቶ ጨርቋን ጥላ ይለይላታል ወይንም እዛው መኝታ ቤት ውስጥ እራሷን አጥፍታ ከአባቷ ጋር ወደመቃብር ትጓዛለች..ከሁለቱ የተለየ የነገ ዕጣ ፋንታ የላትም….
ንስሯ ይዞላት የመጣው ታሪክ ይሄ ነው..በእውነት ልብ የሚነካ ታሪክ ነው…‹‹እና እንዴት ልረዳት እችላለሁ…...?›ስትል እራሷን ጠየቀች፡መቼስ ምንም ተአምረኛ ብትሆን ከሞተ አራት ቀን የሆነው እና በፍሪጅ ውስጥ በቅዝቃዜ የደረቀ ሬሳን ህይወቱን ካሄደችበት መልሳ በማዋሀድ ነፍስ ልትዘራበት አትችልም…ይሄ የማይቻል ነው… ቢሆንም ቢያንስ ልጅቷ የአባቷን ሞት አምና እንድትቀበል እና እንድትቀብረው…ከዛም እንድትጽናና የሚያስችል አንድ ዘዴ መዘየድ እንዳለባት ተሰማት…አዎ ያንን ማድረግ ትፈልጋለች…
ሀሳቧን ሰብስባ ውሳኔ ላይ ሳትደርስ በፊት የሳሎኗ በራፍ ተንኳኳ..ግራ ገባት …በዚህ ጥዋት ማን ነው የሚያንኳኳው .. ..?ገና አንድ ሰዓት እንኳን አልሆነም፡፡
‹‹…ማነው..?››ከተቀመጠችበት ሳትነሳ
‹‹እኔ ነኝ ..››
የፕሮፌሰር ድምጽ ነው..ተነሳችና ከፈተችላቸው‹‹እንዴ ፕሮፌሰር..በጥዋት እንዴት ተነሱ..?››
‹‹አረ ጨርሶውኑም አልተኛሁም…ከሰው ጋር ስለሆንሽ ነው እንጂ ለሊቱን አብሬሽ ስጫወት ማደር ነበር የፈለግኩት››
‹‹ምነው በሰላም..?››
‹‹እኔ እንጃ ብቻ ትናፍቂኛለሽ…ከፍቶኛል››
‹‹እንዴ ፕሮፌሰር..እስቲ ግቡ››
‹‹አሁን አልገባም.. በኋላ ግን እፈልግሻልሁ››
‹‹ለምን አይገቡም..?››
‹‹አይ አሁን እንግዳ ይፈልግሻል››
‹‹ማንን እኔን....?››ግራ ገብቷት
‹‹አዎ አንቺን››ብለው ከበራፍ ላይ ገለል ሲሉ ከጀርባቸው በአዕምሮዋ ውስጥም የሌለ ሰው ብቅ አለ…አንድ ጥቁር ሻንጣ በእጁ አንጠልጥሎ አንገቱን ደፍቶ ቋማል..ፕሮፌሰሩ ወደክፍላቸው ተመለሱ….
‹‹እንዴ መላኩ ..ምነው ሰላም አይደለህም እንዴ....?ሰሚራን አመማት እንዴ..?››
‹‹አረ እሷስ ደህና ነች››
‹‹ታዲያ ምነው በለሊት....?››እስቲ ግባ ብላ ወደውስጥ ገብቶ እንዲቀመጥ አደረገችው…
‹‹ምን ሆንክ..?››ፊት ለፊቱ ቆማ በገረሜታ እያየቸችው ዳግመኛ የመጣበትን ምክንያት ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን ያልሆንኩት ነገር አለ..አሸንፈሻል …ሰሚርን አስመርምሬያታለሁ..ሙሉ በሙሉ ጤነኛ ሆናለች..››
‹‹አሪፍ ነዋ .ታዲያ ደስ አላለህም..?››
‹‹አዎ ብሎኛል…››
‹‹እና ታዲያ አሁን ለምን መጣህ..?››
‹‹ስምምነታችንን ላከብር ነዋ..በሶስት ቀን ውስጥ ትተሀት ካልመጣህ ብለሽ ፎክረሻ አድራሻሽን ሰጥተሸኝ ነበር እኮ..የሆነ ነገር ለማድረግ ኃይል እንዳለሽ አሳይተሸኛል…እንቢ ብዬ በዛው ብቀር ደግሞ ፍቅሬን መልሰሽ በሽተኛ ብታደርጊብኝስ..?››
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
የንስሯ ጭንቅላቷ ላይ ማረፍ ነበር ከእንቅልፏ ያባነናት….በመከራ አይኗን ገልጣ ዙሪያዋን ስትቃኝ እራሷን እዛው ቅድም የተዘረረችበት ወለል ላይ እርቃኗን አገኘችው….ባለ ላደውም የሞተ እስኪመስል ድረስ ትንፋሹ ጠፍቶ እግሮቾ መካከል ጭንቅላቱን ቀብሮ በተመሳሳይ እርቃኑን ተዘርሯል ….ቀስ ብላ ከላዮ ላይ ገልበጥ አደረገችውና እና እራሷን በማላቀቅ ሾልካ ወደ ሻወር በመሄድ ለ5 ደቅቃ ውሃ በላይዋ ላይ አፈሰሰችና..
ከዛ ወደመኝታ ቤቷ ተመልሳ ቢጃማ ለበሰችና ባለ ላዳውን እንደምንም እየጎተተችም እየደገፈችውም ወስዳ አልጋው ላይ በማስተኛት ብርድልብስ ካለበስችው በኋላ ወደሳሎን አመራች…..ንስሯም ተከተላት..፡፡
አዎ ሊነጋ መሆኑን ከውጭ የሚሰማውን የወፎች ዝማሬ በማዳመጥ ተረዳች …ሳሎኖ እንደደረሰች ተስተካክላ ከተቀመጠች በኋላ ንስሯ ያየውን እንዲያሳየት… ያወቀውን እንዲያሳውቃት አዕምሮዋን ከእሱ ጋ አቆራኘችው…
ሰላምና አባቷ…ፍቅራቸው ከአባትና ከልጅም የዘለል አይነት ነው..ኤርምያስ እንዳለው እናትም አባትም ወንድምም እህትም ሆነው ነው ያሳደጎት…ግን አሁን ስላለችበት ሁኔታ ብቻ ያለውን ታሪክ ከንስሯ በተረዳችው የሚከተለውን ነው
ቀጥታ ቤታቸው ገባች… መኝታ ቤት ወደመሰላት ክፍል ተጓዘች… አዎ ትክክል ነች ያልተነጠፈ እና የተዝረከረከ አልጋ … አልጋው ላይ የተዘረረች ውብ ለጋ ሀዘን የሰበራት ወጣት ተኝታለች…..ወለሉ ጠቅላላ በመጠጥ ጠርሙሶች እና በተበታተኑት ልብሶች ተሞልቷል..አንድ ግዙፍ አራት መአዘን ፍሪጅ አልጋውን ተደግፎ ይታያል…ትኩረቷን ወደፍሪጁ አመዘነበት… ውስጡን አየችው… .ህልም ውስጥ ነኝ እንዴ ያስብላል… …ነጭ ሱፍ ለብሶ ነጭ ሸሚዝና ቀይ ከረባት ያደረገ እንቅልፍ የተኛ የሚመስል ሰው ፍሪጅ ውስጥ ይታያል.. ..አባቷ ነው ….የሰላም አባት..አሁን የሆነ ነገር የገባት ነው..ልጅቷ እንደጠረጠረችውም አደጋ ላይ ነች…ሰላም አባቷን አጥታለች..ሰላም አባቷን መሬት ውስጥ ቀብራ ለዘላላም ለመለየት ድፍረቱንም ጭካኔውንም ለማግኘት አልቻለችም….
/////
ነገሩን በዝርዝር ለመረዳት አምስት ቀን ወደኃላ እንመለስ
እንደማንኛውም ቀን እየተጎራረሱ እራት በሉ…እያተሳሳቁ ዜናና ፊልም አዩ…አራት ሰዓት አካባቢ ወደመኝታቸው አመሩ….ሰላም አባቷን መኝታ ቤት አስገብታ እንዲተኙ ካደረገች በኃላ ግንባራቸውን ስማ ተሰናብታ ወደመኝታዋ ልትሄድ ስትል
‹‹ሰላሜ››ሲሉ ጠሯት
‹‹አቤት አባ›››
‹‹አብረሺኝ ተኚ››
ዘላ አልጋው ላይ ወጣችን ብድርብሱን ገልጣ ከውስጥ በመግባት እቅፋቸው ውስጥ ገባች…..ይህ አዲስ ነገር አይደለም..ተለያይተው ከሚተኙበት ይልቅ አንድ ላይ የሚተኙባቸው ቀናቶች የበዙ ነበሩ..ሁለቱም ትንሽ ሲከፋቸው ወይንም አመም ሲያደርጋቸው..ወይንም እንዲሁ ለብቻ መተኛት ሲደብራቸው ዛሬ እኔ ጋር ትተኚ..?ዛሬ አብረሀኝ ትተኛ..? እየተባባሉ አንድ ቀን እሷ ክፍል አንድ ቀን እሳቸው ክፍል ይተኛሉ..እና የተለመደ ነው፡፡
ችግሩ ንጊ ላይ ከእንቅልፏ ባና ከእቅፋቸው ስትወጣ ነበር የተፈጠረው….እጃቸውን ከሰውነቷ ላይ ሳታነሳ በተለየ ሁኔታ ቀዘቀዛት…..ቀስ ብለ ወጣችና አየቻቸው..ጸጥ ያለ ፊት ነበር..ዝም ያለ ፊት…እጇን ወደ አንገታቸው ላከች ….ትንፋሽ አልባ ሆነዋል..
‹‹አባዬ ..አባዬ›› ወዘወዘቻቸው…ጮኸች……..ወደመኝታ ቤቷ በሩጫ ሄደችና የልብ ማዳመጫ መሳሪዋን አመጣች…ምንም የለም..?…ጮኸች…ሁሉ ነገር ረፍዶ ነበር..ፀሀይ በጠለቀችበት ቀርታ ነበር…ጨረቃ በደመናው ሙሉ በሙሉ ተሸንፋ ከስማ ነበር…ምጽአት ደርሶ ነጋሪት እየተጎሰመ እና መለከት እየተነፋ ነበር…..
አባቷ እርግጥ ህመም ላይ ከነበሩ ወራት አልፏቸዋል….ግን እየተንከባከበቻቸው እና በትክክል የህክምና ክትትል እያደረገችላቸው ነበረ…ምንም የተለየ እና ለሞት የሚያሰጋ ምልክት አልተመለከተችም….የት ጋር ነው የተሸወደችው…..?ማወቅ አልቻለችም…፡፡ ለሳዕታት እሬሳውን ላይ ተኝታ ስትነፈርቅ ቆየች…ስልክ ደውላ ለወዳጆቾ ልትናገር ፈለገችና መደወል ከጀመረች በኃላ መልሳ ተወችው
‹‹አባቴን ልቀብር…..?አባቴንም ፈጽሞ አልቀብርም…….ለሳዕታት ካሰበች በኃላ ወሰነች‹‹..አብሬው እሞታለሁ..ግን ለመሞት እስክቆርጥ ድረስ እሱም አይቀበርም›› አለችና…ባላት የህክምና እውቀት በመጠቀም ሬሳው እንዳይበሰብስ አድርጋ በባለመስታወት ፍሪጅ ውስጥ በማድረግ መኝታ ቤት ውስጥ ሬሳውን ደብቃ አስቀመጠች….እና ይሄ ነው የሚያስጨንቃት…እና በዚህ ጊዜ ነበር ኤርምያስ ላዳ ውስጥ የገባችው….ይሄን ችግር ነበር እሱ ሊያውቅና ሊረዳላት ያልቻለው…..በዚህ ከቀጠለች በጥቂት ቀናት ውስጥ ወይ አዕምሮዋ ተነክቶ ጨርቋን ጥላ ይለይላታል ወይንም እዛው መኝታ ቤት ውስጥ እራሷን አጥፍታ ከአባቷ ጋር ወደመቃብር ትጓዛለች..ከሁለቱ የተለየ የነገ ዕጣ ፋንታ የላትም….
ንስሯ ይዞላት የመጣው ታሪክ ይሄ ነው..በእውነት ልብ የሚነካ ታሪክ ነው…‹‹እና እንዴት ልረዳት እችላለሁ…...?›ስትል እራሷን ጠየቀች፡መቼስ ምንም ተአምረኛ ብትሆን ከሞተ አራት ቀን የሆነው እና በፍሪጅ ውስጥ በቅዝቃዜ የደረቀ ሬሳን ህይወቱን ካሄደችበት መልሳ በማዋሀድ ነፍስ ልትዘራበት አትችልም…ይሄ የማይቻል ነው… ቢሆንም ቢያንስ ልጅቷ የአባቷን ሞት አምና እንድትቀበል እና እንድትቀብረው…ከዛም እንድትጽናና የሚያስችል አንድ ዘዴ መዘየድ እንዳለባት ተሰማት…አዎ ያንን ማድረግ ትፈልጋለች…
ሀሳቧን ሰብስባ ውሳኔ ላይ ሳትደርስ በፊት የሳሎኗ በራፍ ተንኳኳ..ግራ ገባት …በዚህ ጥዋት ማን ነው የሚያንኳኳው .. ..?ገና አንድ ሰዓት እንኳን አልሆነም፡፡
‹‹…ማነው..?››ከተቀመጠችበት ሳትነሳ
‹‹እኔ ነኝ ..››
የፕሮፌሰር ድምጽ ነው..ተነሳችና ከፈተችላቸው‹‹እንዴ ፕሮፌሰር..በጥዋት እንዴት ተነሱ..?››
‹‹አረ ጨርሶውኑም አልተኛሁም…ከሰው ጋር ስለሆንሽ ነው እንጂ ለሊቱን አብሬሽ ስጫወት ማደር ነበር የፈለግኩት››
‹‹ምነው በሰላም..?››
‹‹እኔ እንጃ ብቻ ትናፍቂኛለሽ…ከፍቶኛል››
‹‹እንዴ ፕሮፌሰር..እስቲ ግቡ››
‹‹አሁን አልገባም.. በኋላ ግን እፈልግሻልሁ››
‹‹ለምን አይገቡም..?››
‹‹አይ አሁን እንግዳ ይፈልግሻል››
‹‹ማንን እኔን....?››ግራ ገብቷት
‹‹አዎ አንቺን››ብለው ከበራፍ ላይ ገለል ሲሉ ከጀርባቸው በአዕምሮዋ ውስጥም የሌለ ሰው ብቅ አለ…አንድ ጥቁር ሻንጣ በእጁ አንጠልጥሎ አንገቱን ደፍቶ ቋማል..ፕሮፌሰሩ ወደክፍላቸው ተመለሱ….
‹‹እንዴ መላኩ ..ምነው ሰላም አይደለህም እንዴ....?ሰሚራን አመማት እንዴ..?››
‹‹አረ እሷስ ደህና ነች››
‹‹ታዲያ ምነው በለሊት....?››እስቲ ግባ ብላ ወደውስጥ ገብቶ እንዲቀመጥ አደረገችው…
‹‹ምን ሆንክ..?››ፊት ለፊቱ ቆማ በገረሜታ እያየቸችው ዳግመኛ የመጣበትን ምክንያት ጠየቀችው፡፡
‹‹ምን ያልሆንኩት ነገር አለ..አሸንፈሻል …ሰሚርን አስመርምሬያታለሁ..ሙሉ በሙሉ ጤነኛ ሆናለች..››
‹‹አሪፍ ነዋ .ታዲያ ደስ አላለህም..?››
‹‹አዎ ብሎኛል…››
‹‹እና ታዲያ አሁን ለምን መጣህ..?››
‹‹ስምምነታችንን ላከብር ነዋ..በሶስት ቀን ውስጥ ትተሀት ካልመጣህ ብለሽ ፎክረሻ አድራሻሽን ሰጥተሸኝ ነበር እኮ..የሆነ ነገር ለማድረግ ኃይል እንዳለሽ አሳይተሸኛል…እንቢ ብዬ በዛው ብቀር ደግሞ ፍቅሬን መልሰሽ በሽተኛ ብታደርጊብኝስ..?››
👍120❤10🥰1👏1🎉1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹ልሄድ ነበር››አላት ሚለው ጠፍቶት..አንዴ ኬድሮንን አንዴ ከፊት ለፊቴ የተቀመጠውን መላኩን እያየ
‹‹አይ መኝታ ቤት ተመልሰህ ትጠብቀኝ..አብረን ነው ምንወጣው››
ግር አለው‹‹ይቅርታ አልሰማሁሽም..?››
‹‹እሱን ልሸኝና እመጣለሁ …መኝታ ቤት ተመልሰህ ጠብቀኝ…››
ባለማመን ወደኋላው ዞረና.. ወደመኝታ ቤት ተመለሰ
ከመላኩ ፊት ላይ ግራ የመጋባት ጥያቄ ስላነበበች‹‹ባለቤቴ ነው..?›› አለችና ሳይጠይቃት መለሰችለት….
‹‹እንዴ….ባለቤቴ…ታዲያ እኔን…....?››
‹‹እኔ ለቀልድ ነበር እደዛ ያልኩህ ..የእውነት ታዳርገዋለህ አላልኩም ነበር…..››ከተቀመጠበት ተነስቶ ተንደርድሮ ጉንጯን እያገላባጠ ሞጨሞጫት
‹‹በእውነት በጣም ነው ደስ ያለኝ…በቃ ሁለቴ ህይወት ሰጥተሸኝል….ሰሚርን አዳንሺልኝ አሁን ደግሞ ነፃነቴን ስትሰጪኝ››
‹‹አይ ግድ የለም››አለችና ከእቅፉ እየወጣች…ጭምቅ አርጎ ሲያቅፈትና ሲስማት መተንፈስ አቅቶት ነበር…በቃ በሽታዋ ሁሉ ሊነሳባት እና ሀሳቧን ልትቀይር ትንሽ ነበር የቀራት…..
እንደመደንገጥ አለና ወደመኝታ ቤቱ ገልመጥ በማለት ሲስማት ማንም እንዳላየው ለማጣራት ሲሞክር በቆረጣ አይታ ለራሷ ፈገግ አለች ..‹‹በቃ ልሂድ.. ሌላ ቀን ከሰሚር ጋር መጥተን እንጠይቅሻለን ….በቃ ዘመድ እንሆናለን..››እያለ ይዞ የመጣውን ሻንጣ ይዞ ለመሄድ አንጠልጠሎ ተዘጋጀ፡፡
‹‹ሰላም በልልኝ..ግን እኔን ለመጠየቅ አትልፉ.. ዛሬ ለሊት ወደውጭ ልበር ነው….››ስትል ዋሸችው
‹‹ዉይ !!!ምነው?በሰላም..?››እንደመደንገጥ ብሎ፡፡
‹‹አይ በሰላም ነው …ቤተሰብ እዛ ስለሆነ እዛ ለመኖር ነው››
‹‹እሺ በቃ እግዜር ካንቺ ጋር ይሁን …ዕድሜ ልክ ከፍዬ የማልጨርሰው ውለታሽ አለብኝ ››እያለ ሳሎኑን ባለማመን ለቆ ወጣ……
‹‹ምን ያህል መስዋዕትነት እንደከፈልኩልህ ብታውቃው..ባንተ ምክንያት ይህቺን አለምና ንስሬንም ጭምር እንደአጣሁ ብትሰማ›› ስትል አሰበች
….ይህን ሁሉ ልትነግረው ያልፈለገችው ቢያንስ በስተመጨረሻ ጥሩ ልሁንለት ብላ ነው ….በፀፀት ያልደፈረሰ የፍቅር ህይወት ይገባዋል ብላ ስላሰበች ነው….አሁን የእነሱን ሰሚራ ለማዳን የሆነችውን እና ያጣችውን ዘርዝራ ባታወራው ከማዘን በስተቀር ለእሷ ምንም አይፈይድላትም..በእሱ ህይወት ላይ ግን ቁጭትን ይፈጥርበታል…..ደስታው ላይ ደመና ያጠላል…. ያንን አስባ ነው እውነቱን የደበቀችው፡፡
/////
ሀሳቧን ሰብስባ ቀጥታ ወደመኝታ ቤቴ ሄደች…. ስትደርስ ባዶ ነው..ግራ ገባት….‹‹ እንዴ በጓሮ በር ሾልኮ ፈረጠጠ እንዴ..? ››ብላ ሳታሰላስል ከሻወር ቤት የውሃ መንሾሾት ድምጽ ሰማችና ወደ እዛው ሄደች..ደረሰችና ብርግድ አድርጋ ከፈተችው…. ድንገት መሳሪያ እንደተደቀነበት ምርኮኛ ኩም ብሎ ደነገጠ..እጆቹን የተንዘላዘለ እንትኑ ላይ ሸፈናቸው….
‹‹አረ ልቀቀው ..ለሊቱን እስክጠግብ እኮ ሳየው ነው ያደርኩት››
‹‹እብድ ነሽ..አስደነገጥሸኝ እኮ …››አለና ቀስበቀስ ለቀቀው
‹‹ህፃን ሆነህ እናትህ በቂቤ በደንብ ያሹልህ እና ይጎትቱልህ ነበር እንዴ..? ››
‹‹‹ምን እንዲሆን ነው የምትጎትትልኝ..?››
‹‹እንዲህ እንዲንጀላጀል ነዋ….ሜትር ከምናምን እንዲሆንልህ››
‹‹ትቀልጂያለሽ..ቆይ ማን ነበር ሰውዬው… ውሽማሽ መስሎኝ እኮ ተበላሁ ብዬ ነበር››
‹‹አይደለም ዘመዴ ነው…እንዴት ነው እኔም አወላልቄ ልግባ እንዴ..?››
‹‹ወዴት....?››
‹‹ወደሻወር ነዋ..እጠበኝ ልጠብህ››
‹‹ኸረ በፈጠረሽ..ስወደሽ እንዳታደርጊው››
ሳቋ አመለጠት‹‹እንዴ !!ይሄን ያህል…...?››
‹‹እንዴ…እሳት እኮ ነሽ…እኔ እንጃ የዛሬ ወር ድረስ ተከፍቶ ባገኝ እንኳን ለመክደን አልሞክርም…እንዴት እንዴት አይነት የወሲብ ጥብብ ነው..የሆነ ህልም ውስጥ እኮ ነው ያስገባሺኝ..በአየር ላይ ሁሉ እየተንሳፈፍኩ ይመስለኛል…አሁን ሳስበው ደግሞ እንዴት በአየር ላይ መንሳፈፍ ይቻላል እላለው....?ከግድግዳ ጋር ግን እዳጣበቅሺኝ በእርግጠኝነት አውቃለሁ..ግን አጥንቶቼ ስብርባራቸው ለምን እንዳልወጣ እንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ…ብቻ ግራ ተጋብቻለሁ.፡፡እኔ በህይወት ፍቅር እንጂ ያጣሁት የወሲብ ችግር ገጥሞኝ አያውቅም….ቁጥራቸውን ከማላስታውሳቸው ሴቶች ጋር ወሲብ ፈጽሜያለሁ..በአንድ ለሊት ስድስት ሰባቴ …ግን ከንቺ ጋር ያደረኩት አንድ ዙር ወሲብ እድሜ ልኬን ከደረኩት ጋር የማይነፃፀር እና የተለየ ነው››
‹‹ወሲብ ደጋግመን የምፈፅመው ለምን እንደሆነ ታውቃልህ..?››
‹‹እኔ እንጃ››
‹‹እኔ ግን ስገምት ..ለኮፍ ለኮፍ ከሆነ ወዲያው ወዲያው ያምርሀል…በሁለት ደቂቃ በራፍ ላይ ደፍቶ ተልኮውን የሚያጠናቅቅ ሰውና በ20 ደቂቃ ውስጠ ውስጥ በርብሮ ግዳጁን ያጠናቀቀ እኩል መልሶ አያሰኛቸውም….ለዛ ነው ››
‹‹ይሁንልሽ ››አለና የሻወሩን ውሃ ዘግቶ… ፎጣውን አገለደመና ከሻወሩ ቤት ወጣ …ተከተለችውና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለች፡፡
‹‹እሺ ቁርስ ትጋብዘኛለህ አይደል..?››አለቸው
‹‹አንቺን ለመሰለች ቆንጆ እንኳን ቁርስ አራሴንስ ብጋብዝሽ ቅር አይለኝም..››
‹‹እራስህንማ እንዴት ልትጋብዘኝ ትችላለህ…..?››
‹‹ለምን አልችልም..?››ሲል ጠየቃት ኮስተር ብሎ
‹‹እኔ ልቡን ለሌላ ሰው ጠቅልሎ ያስረከበና ቀፎውን ብቻ ያለ ሰው ምን ያደርግልኛል…....?››
‹‹አይ የምታወሪው ስለ ሰላም ከሆነ ተስፋ ቆርጬያለሁ….አሁን የምፈለገው ምን እንደሆነች ብቻ አውቄ ልረዳት ነው…ያንን ማድረግ ከቻልኩ ይበቃኛል…ካዛ….››
‹‹ከዛ ምን…..?››
‹‹እኔ እንጃ… የላዳ ሹፌር ነው ብለሽ ካልናቅሺኝ በጣም ነው ያፈቀርኩሽ..?››
‹‹ያፈቀርኩሽ ስትል..?››
‹‹ያፈቀርኩሽ ነዋ..በጣም ነው የተመቸሺኝ ….የሆነ የማላውቀውን አለም ነው ያሳየሺኝ…ላጣሽ አልፈልግም….››
‹‹ስለእኔ ምንም እኮ አታውቅም....?››
‹‹ማወቅ አልፈልግም..አንቺ ብቻ እሺ በይኝ እንጂ…..››ንግግሩን ሳይጨርስ ንስሯ እየበረረ የመኝታ ቤቱን በር በርግዶ በመግባት እንደቀናተኛ አባ ወራ አልጋ ላይ ተኮፍሶ ጉብ አለ….
ይሄንን በድንገት ያየው ባለ ላዳው ከተቀመጠበት በርግጎ ወድቆ ነበር..
‹‹አይዞህ አይዞህ…›››ሳቋ እያመለጣት
‹‹አይዞህ….!!›
‹‹የማታው ንስር አይደል..?››
‹‹አዎ ነው››
‹‹ምን ይሰራል እዚህ..?››
‹‹እዚህ ምን ትሰራለህ ..?ብሎ መጠየቅ ያለበት እሱ ነው..ምክንያም እሱ የገዛ ቤት ውስጥ ነው ያለው››
‹‹ማታ የእኔ ነው ያልሺው እወነትሽን ነው እንዴ..?››
‹‹አይ የእኔ አይደለም..እኔ ነኝ የእሱ….››
‹‹እኔ እንጃ ግራ ይገባል..››እያለ ልብሱን መልበስ ጀመረ……..
‹‹ሰላምን እንድትረዳት ልናግዝህ እንችላለን››አልኩት
‹‹ልናግዝህ ስትይ....?አንቺና ማን..?››
‹‹እኔና ንስሬ››
ፈገግ አለ….‹‹ትቀልጂብኛለሽ አይደል..?››
‹‹የምሬን ነው…›
‹‹አንቺ እሺ ይሁን …ይሄ እንስሳ እንዴት አድርጎ ነው የሚረዳኝ..ደግሞስ አንቺስ ብትሆኚ በምን መልኩ ልትረጀኝ ትችያለሽ .. ..?እኔ እንኳን ገና ችግሯን ማወቅ አልቻልኩም››
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹ልሄድ ነበር››አላት ሚለው ጠፍቶት..አንዴ ኬድሮንን አንዴ ከፊት ለፊቴ የተቀመጠውን መላኩን እያየ
‹‹አይ መኝታ ቤት ተመልሰህ ትጠብቀኝ..አብረን ነው ምንወጣው››
ግር አለው‹‹ይቅርታ አልሰማሁሽም..?››
‹‹እሱን ልሸኝና እመጣለሁ …መኝታ ቤት ተመልሰህ ጠብቀኝ…››
ባለማመን ወደኋላው ዞረና.. ወደመኝታ ቤት ተመለሰ
ከመላኩ ፊት ላይ ግራ የመጋባት ጥያቄ ስላነበበች‹‹ባለቤቴ ነው..?›› አለችና ሳይጠይቃት መለሰችለት….
‹‹እንዴ….ባለቤቴ…ታዲያ እኔን…....?››
‹‹እኔ ለቀልድ ነበር እደዛ ያልኩህ ..የእውነት ታዳርገዋለህ አላልኩም ነበር…..››ከተቀመጠበት ተነስቶ ተንደርድሮ ጉንጯን እያገላባጠ ሞጨሞጫት
‹‹በእውነት በጣም ነው ደስ ያለኝ…በቃ ሁለቴ ህይወት ሰጥተሸኝል….ሰሚርን አዳንሺልኝ አሁን ደግሞ ነፃነቴን ስትሰጪኝ››
‹‹አይ ግድ የለም››አለችና ከእቅፉ እየወጣች…ጭምቅ አርጎ ሲያቅፈትና ሲስማት መተንፈስ አቅቶት ነበር…በቃ በሽታዋ ሁሉ ሊነሳባት እና ሀሳቧን ልትቀይር ትንሽ ነበር የቀራት…..
እንደመደንገጥ አለና ወደመኝታ ቤቱ ገልመጥ በማለት ሲስማት ማንም እንዳላየው ለማጣራት ሲሞክር በቆረጣ አይታ ለራሷ ፈገግ አለች ..‹‹በቃ ልሂድ.. ሌላ ቀን ከሰሚር ጋር መጥተን እንጠይቅሻለን ….በቃ ዘመድ እንሆናለን..››እያለ ይዞ የመጣውን ሻንጣ ይዞ ለመሄድ አንጠልጠሎ ተዘጋጀ፡፡
‹‹ሰላም በልልኝ..ግን እኔን ለመጠየቅ አትልፉ.. ዛሬ ለሊት ወደውጭ ልበር ነው….››ስትል ዋሸችው
‹‹ዉይ !!!ምነው?በሰላም..?››እንደመደንገጥ ብሎ፡፡
‹‹አይ በሰላም ነው …ቤተሰብ እዛ ስለሆነ እዛ ለመኖር ነው››
‹‹እሺ በቃ እግዜር ካንቺ ጋር ይሁን …ዕድሜ ልክ ከፍዬ የማልጨርሰው ውለታሽ አለብኝ ››እያለ ሳሎኑን ባለማመን ለቆ ወጣ……
‹‹ምን ያህል መስዋዕትነት እንደከፈልኩልህ ብታውቃው..ባንተ ምክንያት ይህቺን አለምና ንስሬንም ጭምር እንደአጣሁ ብትሰማ›› ስትል አሰበች
….ይህን ሁሉ ልትነግረው ያልፈለገችው ቢያንስ በስተመጨረሻ ጥሩ ልሁንለት ብላ ነው ….በፀፀት ያልደፈረሰ የፍቅር ህይወት ይገባዋል ብላ ስላሰበች ነው….አሁን የእነሱን ሰሚራ ለማዳን የሆነችውን እና ያጣችውን ዘርዝራ ባታወራው ከማዘን በስተቀር ለእሷ ምንም አይፈይድላትም..በእሱ ህይወት ላይ ግን ቁጭትን ይፈጥርበታል…..ደስታው ላይ ደመና ያጠላል…. ያንን አስባ ነው እውነቱን የደበቀችው፡፡
/////
ሀሳቧን ሰብስባ ቀጥታ ወደመኝታ ቤቴ ሄደች…. ስትደርስ ባዶ ነው..ግራ ገባት….‹‹ እንዴ በጓሮ በር ሾልኮ ፈረጠጠ እንዴ..? ››ብላ ሳታሰላስል ከሻወር ቤት የውሃ መንሾሾት ድምጽ ሰማችና ወደ እዛው ሄደች..ደረሰችና ብርግድ አድርጋ ከፈተችው…. ድንገት መሳሪያ እንደተደቀነበት ምርኮኛ ኩም ብሎ ደነገጠ..እጆቹን የተንዘላዘለ እንትኑ ላይ ሸፈናቸው….
‹‹አረ ልቀቀው ..ለሊቱን እስክጠግብ እኮ ሳየው ነው ያደርኩት››
‹‹እብድ ነሽ..አስደነገጥሸኝ እኮ …››አለና ቀስበቀስ ለቀቀው
‹‹ህፃን ሆነህ እናትህ በቂቤ በደንብ ያሹልህ እና ይጎትቱልህ ነበር እንዴ..? ››
‹‹‹ምን እንዲሆን ነው የምትጎትትልኝ..?››
‹‹እንዲህ እንዲንጀላጀል ነዋ….ሜትር ከምናምን እንዲሆንልህ››
‹‹ትቀልጂያለሽ..ቆይ ማን ነበር ሰውዬው… ውሽማሽ መስሎኝ እኮ ተበላሁ ብዬ ነበር››
‹‹አይደለም ዘመዴ ነው…እንዴት ነው እኔም አወላልቄ ልግባ እንዴ..?››
‹‹ወዴት....?››
‹‹ወደሻወር ነዋ..እጠበኝ ልጠብህ››
‹‹ኸረ በፈጠረሽ..ስወደሽ እንዳታደርጊው››
ሳቋ አመለጠት‹‹እንዴ !!ይሄን ያህል…...?››
‹‹እንዴ…እሳት እኮ ነሽ…እኔ እንጃ የዛሬ ወር ድረስ ተከፍቶ ባገኝ እንኳን ለመክደን አልሞክርም…እንዴት እንዴት አይነት የወሲብ ጥብብ ነው..የሆነ ህልም ውስጥ እኮ ነው ያስገባሺኝ..በአየር ላይ ሁሉ እየተንሳፈፍኩ ይመስለኛል…አሁን ሳስበው ደግሞ እንዴት በአየር ላይ መንሳፈፍ ይቻላል እላለው....?ከግድግዳ ጋር ግን እዳጣበቅሺኝ በእርግጠኝነት አውቃለሁ..ግን አጥንቶቼ ስብርባራቸው ለምን እንዳልወጣ እንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ…ብቻ ግራ ተጋብቻለሁ.፡፡እኔ በህይወት ፍቅር እንጂ ያጣሁት የወሲብ ችግር ገጥሞኝ አያውቅም….ቁጥራቸውን ከማላስታውሳቸው ሴቶች ጋር ወሲብ ፈጽሜያለሁ..በአንድ ለሊት ስድስት ሰባቴ …ግን ከንቺ ጋር ያደረኩት አንድ ዙር ወሲብ እድሜ ልኬን ከደረኩት ጋር የማይነፃፀር እና የተለየ ነው››
‹‹ወሲብ ደጋግመን የምፈፅመው ለምን እንደሆነ ታውቃልህ..?››
‹‹እኔ እንጃ››
‹‹እኔ ግን ስገምት ..ለኮፍ ለኮፍ ከሆነ ወዲያው ወዲያው ያምርሀል…በሁለት ደቂቃ በራፍ ላይ ደፍቶ ተልኮውን የሚያጠናቅቅ ሰውና በ20 ደቂቃ ውስጠ ውስጥ በርብሮ ግዳጁን ያጠናቀቀ እኩል መልሶ አያሰኛቸውም….ለዛ ነው ››
‹‹ይሁንልሽ ››አለና የሻወሩን ውሃ ዘግቶ… ፎጣውን አገለደመና ከሻወሩ ቤት ወጣ …ተከተለችውና አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለች፡፡
‹‹እሺ ቁርስ ትጋብዘኛለህ አይደል..?››አለቸው
‹‹አንቺን ለመሰለች ቆንጆ እንኳን ቁርስ አራሴንስ ብጋብዝሽ ቅር አይለኝም..››
‹‹እራስህንማ እንዴት ልትጋብዘኝ ትችላለህ…..?››
‹‹ለምን አልችልም..?››ሲል ጠየቃት ኮስተር ብሎ
‹‹እኔ ልቡን ለሌላ ሰው ጠቅልሎ ያስረከበና ቀፎውን ብቻ ያለ ሰው ምን ያደርግልኛል…....?››
‹‹አይ የምታወሪው ስለ ሰላም ከሆነ ተስፋ ቆርጬያለሁ….አሁን የምፈለገው ምን እንደሆነች ብቻ አውቄ ልረዳት ነው…ያንን ማድረግ ከቻልኩ ይበቃኛል…ካዛ….››
‹‹ከዛ ምን…..?››
‹‹እኔ እንጃ… የላዳ ሹፌር ነው ብለሽ ካልናቅሺኝ በጣም ነው ያፈቀርኩሽ..?››
‹‹ያፈቀርኩሽ ስትል..?››
‹‹ያፈቀርኩሽ ነዋ..በጣም ነው የተመቸሺኝ ….የሆነ የማላውቀውን አለም ነው ያሳየሺኝ…ላጣሽ አልፈልግም….››
‹‹ስለእኔ ምንም እኮ አታውቅም....?››
‹‹ማወቅ አልፈልግም..አንቺ ብቻ እሺ በይኝ እንጂ…..››ንግግሩን ሳይጨርስ ንስሯ እየበረረ የመኝታ ቤቱን በር በርግዶ በመግባት እንደቀናተኛ አባ ወራ አልጋ ላይ ተኮፍሶ ጉብ አለ….
ይሄንን በድንገት ያየው ባለ ላዳው ከተቀመጠበት በርግጎ ወድቆ ነበር..
‹‹አይዞህ አይዞህ…›››ሳቋ እያመለጣት
‹‹አይዞህ….!!›
‹‹የማታው ንስር አይደል..?››
‹‹አዎ ነው››
‹‹ምን ይሰራል እዚህ..?››
‹‹እዚህ ምን ትሰራለህ ..?ብሎ መጠየቅ ያለበት እሱ ነው..ምክንያም እሱ የገዛ ቤት ውስጥ ነው ያለው››
‹‹ማታ የእኔ ነው ያልሺው እወነትሽን ነው እንዴ..?››
‹‹አይ የእኔ አይደለም..እኔ ነኝ የእሱ….››
‹‹እኔ እንጃ ግራ ይገባል..››እያለ ልብሱን መልበስ ጀመረ……..
‹‹ሰላምን እንድትረዳት ልናግዝህ እንችላለን››አልኩት
‹‹ልናግዝህ ስትይ....?አንቺና ማን..?››
‹‹እኔና ንስሬ››
ፈገግ አለ….‹‹ትቀልጂብኛለሽ አይደል..?››
‹‹የምሬን ነው…›
‹‹አንቺ እሺ ይሁን …ይሄ እንስሳ እንዴት አድርጎ ነው የሚረዳኝ..ደግሞስ አንቺስ ብትሆኚ በምን መልኩ ልትረጀኝ ትችያለሽ .. ..?እኔ እንኳን ገና ችግሯን ማወቅ አልቻልኩም››
👍110❤15😁4👏2😱2👎1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/////
ወደቀልቧ እስክትመለስ እና መኝታ ቤቷ ውስጥ ያልጋበዘቻችው ሰዎች እንደገቡ ለመገንዘብ ከአንድ ሰዓት በላይ ወሰደባት ….
‹‹እንዴት ብትደፍረኝ ነው ግን ሰተት ብለህ መኝታ ቤቴ ድረስ ሚስትህን ይዘህ የገባኸው……?.›
ኤርሚያስ ግራ ተጋባ … ተርበተበተ……‹‹ይቅርታ..ማለት ሚስቴ አይደለችም…. አላውቃትም..ይቅርታ ማለቴ አውቃታለሁ ግን ይሄውልሽ እሷ….››
አቋረጠችው ‹‹…ውጣልኝ …ውጡልኝ..››ጭንቅላቷን በእጆቾ ይዛ ጩኸቷን ለቀቀችው….
‹‹እሺ እንወጣለን..አንቺ ብቻ ተረጋጊ… እንወጣለን…ይሄው እየወጣን ነው…››የሚያደርገው ጠፍቶት ክፍሉን ለቆ ለመውጣት ወደበራፉ ፊቱን አዞረ…
ኬድሮን‹‹አባትሽን ላገናኝሽ ነው የመጣሁት››አለቻት
ከተቀመጠችበት ወንበር ንቅንቅ ሳትልል
ከትከት ብላ ሳቀች..የምፀት ሳቅ…..የእብደት ሳቀ..የንዴት ሳቅ
‹‹እንዴት አድርገሽ ነው ከሞተው አባቴ ጋር ምታገናኚኝ….…?ነው ወይስ ከበድኑ ነው ልታገኛኚኝ ያሰብሺው…..አመሰግናለሁ በድኑ በእጄ ስለሆነ አትልፊ ….››
‹‹አይ እዲያናግርሽ ማድረግ እችላለሁ››
‹‹እንዲያናግረሽ አልሽ…..ኤርሚያስ ምን በድዬሀልው..…?››አለችው ወደእሱ ዞራ
እየተርበተበተ‹‹..ሰላም አንቺ ምን በወጣሽ.. አረ ምንም አልበደልሺኝም …ለምን እንደዛ ልትይ ቻልሽ…?››
‹‹እንዴ ያንተ ሳያንስ ሌላ ሰው ይዘህ መጥተህ እድታሾፍብኝ ታደርጋለህ……?በሀዘኔ እንዴት ታላግጣላችሁ….…?በቁስሌ እንዴት ጨው ትነሰንሳላችሁ…?ይሄ ምን አይነት ጭካኔ ነው …?…››
‹‹አረ በፍፅም እንደዛ አይደለም….አንቺን ለመርዳት እንጂ ሌላ ምንም አላማ የለንም››
‹‹እና ታዲያ እንዴት ነው ከአባቴ የምታገናኘኝ……?.››
‹‹እሱን አንዴት እንደሆነ አላውቅም ..ግን ታደርገዋለች ››አለ አንዴ ኬድሮንን አንዴ ሰላምን በማፈራረቅ እያየ
ልታስረዳት ሞከረች‹‹እመኚኝ የሙት መንፈስ ማናገር እና ከሚወዶቸው ሰዎች ጋር የማገናኘት ችሎታ አለኝ…መቼስ ስለዚህ ጉዳይ ሰምተሸ አታውቂም ለማለት አቸገራለው….››
‹‹ሰምቼማ አውቃለው..በመጽሀፍ ቅዱስ ላይም አንብቤያው..ግን ..››>
‹‹ምንም ግን የለም…››ብላ ንስሯን እንዲመጣ በአዕምሮዬ መልዕክት አስተላለፍችለት ….. ክንፉን እየማታ መጣና አልፎን ፈሪጁ ላይ ጉብ ሲል ሰላም በድንጋጤ ተንደርድራ ልትሰፍርበት ስትል ቦታ ቀየረና አመለጣት….
‹‹አባቴን ..አግዙኝ…. አባቴን አንዳይነካብኝ››
‹‹አይዞሽ የእኔ ንስር ነው ..ምንም አያደርግም…››
‹‹እርግጠኛ ነሽ ……?አባቴን አይነካውም…?››አለች… በእሷ ግምት የኬድሮን ንስር የአባቷን በድን አካል ለመዘንጠል ይዳዳል ብላ ነው
‹‹እንዴ ንስር የሞተ ነገር እንደማይነካ አታውቂም…››
‹‹አላውቅም››አለች
‹‹እኔም አላውቅም ››በማለት ድጋፍ ሰጣት ኤልያስ
ማብራሪያዬን በኩራት ቀጠልኩ ‹‹ንስር ኩሩ ነው…እራሱ አባሮ… እራሱ ታግሎ …እራሱ ገድሎ ካልሆነ ነክች አያደርግም…ለማንኛውም አሁን ተዘጋጂ ቁጭ በይ ››….ቁጭ አለች…
‹‹ይሄሁልሽ አሁን ንስሬ ያግዘኝና ከአባትሽ መንፈስ ጋር አገናኝሻለሁ...ማለት የእኔን አንደበት ተጠቅመው አባትሽ ቀጥታ ያናግሩሻል..በእኔ አንደበት በራሳቸው ድምፅ››
‹‹እሺ››
‹‹ኤርምያስ አንተ ደግሞ ካለህበት እንዳትነቃነቅ..ምንም የሚረብሽ ነገር ካለ ትኩረቴን ስለሚበታን መሀል ላይ ግንኙነቱ ሊቋረጥ ይችላል››
‹‹አረ በፍጽም ይሄው ንቅንቅ አልልም..ትንፋሼ እራሱ አይሰማም››አለና በተቀመጠበት ጭብጥብጥ አለ
ሁሉም ነገር ዝግጁ መሆኑን ሳታረጋግጥ አዕምሮዋን ከንሰሯ ጋር አገናኘቸው..ለደቂቃዎች ተመሰጠች …ይሄን ነገር ከዚህ በፊት አድርጋው አታውቅም ‹‹..ግን ማድረግ አያቅተኝም›ስትል በራሷ ተማመነች….አዎ ንስሯ የአባቷን ነፍስ ካለችበት እንድትመጠ እየጋበዘ ነው..ወይ ብዙም አላስቸገራትም ….ቀጥታ አባትዬው በኬድሮን አንደበት ልጃቸውን ማናገር ጀመሩ……
‹‹ልጄ ሰላሜ…››
ባለማመን መለሰች‹‹ወይ አባዬ..››ተንደርድራ ሬሳውን እያየች
‹‹እዛ ለምን ትፍልጊኛለሽ….…?አይ ልጄ ስጋዬ ውስጥ አይደለሁም.. …ግን ደግሞ ወደዘላለም ማረፊያዬም መሄድ አልቻልኩም..ከሁለቱም ሳልሆን በአየር ላይ ተንጠልጥዬ አለሁልሽ፡፡
‹‹ምነው አባዬ……? እኔ ልሰቃይልህ…..እኔ በአየር ላይ ለዘላለም ተንጠልጥዬ ልቅር››
‹‹አይ ለምን ልጄ…? ለምን..…?ለአንቺማ ይሄ አይገባም…ትቼሽ ስለሄድኩ ይቅርታ ልጄ..ምን ላድርግ የአማላክ ጥሪ ነው….እባክሽ ልጄ ከዚህ በላይ እንድሰቃይ አታድርጊኝ…››
‹‹እንዴ አባዬ እኔ አንተን ማሰቃየት…?››
‹‹አዎ እናቴ… እዚህ እቤቴ ውስጥ በድን አካሌን ታቅፈሽ እንደዚህ ሆነሽ እንዴት እፎይ ብዬ ወደዘላለም የሚወስደኝን መንገዴን እቀጥላለሁ..…?አልችልም ልጄ ..አካሌ መሬት ሳይገባ ነፍሴ ወደአምላኮ ልትሄድ ይከብዳታል..ልጄ እባክሽ በአምላክ ስራ ጣልቃ አትግቢ..››
‹‹እንዴት አባ……? እንዴት ጣልቃ ገባሁ……?.››
‹‹እንዴ ሞትን የፈጠረውን አምላክ እኮ እየተቃወምሽው ነው..ተሳስተሀል እያልሺው ነው››
‹‹አዎ ተሳስቷልማ..እንዴት አንድ አባቴን ይነጥቀኛል..…?እንዴት ባዶዬን ያስቀረኛል….…?.››
‹‹አየሽ ልጄ …ሞት እርግጥ በጥፋታችን ምክንያት የተሸለምነው ቅጣታችን ነው…ይሁን እና በዚህ ምድር ለመኖር እስከመጣን ድረስ ሞታችንም በጣም አስፈላጊ ነው..››
‹‹እንዴት አባ .. …?ሞት ደግሞ እንዴት ነው ጠቃሚ የሚሆነው.?››
እግዜር ፈጥሮ ምድር ላይ ቢረሳንስ ምን ይውጠናል….…?አርጅተን መንቀሳቀስ አቅቶን እቤት እስክንቀር…. ቆዳችን እስኪጨማደድ እና ወበታችን እስኪረግፍ ድረስ አልወስዳችሁም ቢለን ማነው የሚጎዳው……?.ጥርሳችን ረግፎ ገንፎ እንኳን ማኘክ እስኪያቅተን ቢተወን …አይናችን ለግሞ የልጅ ልጆቻችንን ከጎረቤቶቻችን ልጆች መለየት እስኪያቅተን ..መኝታ ቤታችን ከሽንት ቤታችን መለየት እስኪሳነን ድረስ ኑሩ ብንባል ሽልማት ነው ቅጣት…ዕርግማን ነው ምርቃት…?››
‹‹እንዴ አባዬ.. …!!!አንተ እኮ ገና ነህ …ሰባ አመት እንኳን አልሆነህም..…?››
‹‹እኮ እግዚያብሄር ይወደኛል ማለት ነዋ..…?ምላሴ ጣዕም መለየት ሳይሳነው፤አይኖቼ ማንበብ ሳያቆሙ ፤እግሮቼ ላምሸው ከዘራ ሳልይዘ አስታወሶኛል…››
‹‹ግን እኮ አባ እኔን ጥለህ ነው የሄድከው…?››
‹‹የሞት መጥፎው ክፍል ያ ነው….አዎ ሁልግዜ የሆነ ነገር ጥለሽ መሄድሽ አይቀርም…ማንም ቢሆን ከዚህ ምድር ሲሰናበት የሆነ ነገር በጅምር ጥሎ መሄዱ የሆነ የሚወደውን ሰው ሳይሰናበት ማምለጡ ያለ እና ግዳጅም ነው….እና ልጄ አንቺ አፈር ካላቀመሺኝ እና በሀዘን መቆራመድሽን እስካላቆምሽ ድረስ ጉዞዬን መጀመር አልችልም… ብጀምርም ቶሎ አልደርስም..ሀዘንሸ ወደኃላ ይስበኛል….ለቅሶሽ መንገዴን እያጨቀየው ያዳልጠኝ እና አላላውስ ይለኛል…..››
‹‹አባ አረ እኔ እንዲህ የበደልኩህ አልመሰለኝም…?››
‹‹በደልሺኝ እኮ አላልኩም.. ግን በቃ..አንዳንዴ መሆን ያለበት ነገር እንዲሆን መተው ነው..ታግለሽ ልታሸኝፊው ከማትችይው ነገር ጋር መታገል ከድካም ውጭ እርባን ያለው ውጤት አያስገኝም ››
‹‹እና ምን ላድርግ አባ…?››
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
/////
ወደቀልቧ እስክትመለስ እና መኝታ ቤቷ ውስጥ ያልጋበዘቻችው ሰዎች እንደገቡ ለመገንዘብ ከአንድ ሰዓት በላይ ወሰደባት ….
‹‹እንዴት ብትደፍረኝ ነው ግን ሰተት ብለህ መኝታ ቤቴ ድረስ ሚስትህን ይዘህ የገባኸው……?.›
ኤርሚያስ ግራ ተጋባ … ተርበተበተ……‹‹ይቅርታ..ማለት ሚስቴ አይደለችም…. አላውቃትም..ይቅርታ ማለቴ አውቃታለሁ ግን ይሄውልሽ እሷ….››
አቋረጠችው ‹‹…ውጣልኝ …ውጡልኝ..››ጭንቅላቷን በእጆቾ ይዛ ጩኸቷን ለቀቀችው….
‹‹እሺ እንወጣለን..አንቺ ብቻ ተረጋጊ… እንወጣለን…ይሄው እየወጣን ነው…››የሚያደርገው ጠፍቶት ክፍሉን ለቆ ለመውጣት ወደበራፉ ፊቱን አዞረ…
ኬድሮን‹‹አባትሽን ላገናኝሽ ነው የመጣሁት››አለቻት
ከተቀመጠችበት ወንበር ንቅንቅ ሳትልል
ከትከት ብላ ሳቀች..የምፀት ሳቅ…..የእብደት ሳቀ..የንዴት ሳቅ
‹‹እንዴት አድርገሽ ነው ከሞተው አባቴ ጋር ምታገናኚኝ….…?ነው ወይስ ከበድኑ ነው ልታገኛኚኝ ያሰብሺው…..አመሰግናለሁ በድኑ በእጄ ስለሆነ አትልፊ ….››
‹‹አይ እዲያናግርሽ ማድረግ እችላለሁ››
‹‹እንዲያናግረሽ አልሽ…..ኤርሚያስ ምን በድዬሀልው..…?››አለችው ወደእሱ ዞራ
እየተርበተበተ‹‹..ሰላም አንቺ ምን በወጣሽ.. አረ ምንም አልበደልሺኝም …ለምን እንደዛ ልትይ ቻልሽ…?››
‹‹እንዴ ያንተ ሳያንስ ሌላ ሰው ይዘህ መጥተህ እድታሾፍብኝ ታደርጋለህ……?በሀዘኔ እንዴት ታላግጣላችሁ….…?በቁስሌ እንዴት ጨው ትነሰንሳላችሁ…?ይሄ ምን አይነት ጭካኔ ነው …?…››
‹‹አረ በፍፅም እንደዛ አይደለም….አንቺን ለመርዳት እንጂ ሌላ ምንም አላማ የለንም››
‹‹እና ታዲያ እንዴት ነው ከአባቴ የምታገናኘኝ……?.››
‹‹እሱን አንዴት እንደሆነ አላውቅም ..ግን ታደርገዋለች ››አለ አንዴ ኬድሮንን አንዴ ሰላምን በማፈራረቅ እያየ
ልታስረዳት ሞከረች‹‹እመኚኝ የሙት መንፈስ ማናገር እና ከሚወዶቸው ሰዎች ጋር የማገናኘት ችሎታ አለኝ…መቼስ ስለዚህ ጉዳይ ሰምተሸ አታውቂም ለማለት አቸገራለው….››
‹‹ሰምቼማ አውቃለው..በመጽሀፍ ቅዱስ ላይም አንብቤያው..ግን ..››>
‹‹ምንም ግን የለም…››ብላ ንስሯን እንዲመጣ በአዕምሮዬ መልዕክት አስተላለፍችለት ….. ክንፉን እየማታ መጣና አልፎን ፈሪጁ ላይ ጉብ ሲል ሰላም በድንጋጤ ተንደርድራ ልትሰፍርበት ስትል ቦታ ቀየረና አመለጣት….
‹‹አባቴን ..አግዙኝ…. አባቴን አንዳይነካብኝ››
‹‹አይዞሽ የእኔ ንስር ነው ..ምንም አያደርግም…››
‹‹እርግጠኛ ነሽ ……?አባቴን አይነካውም…?››አለች… በእሷ ግምት የኬድሮን ንስር የአባቷን በድን አካል ለመዘንጠል ይዳዳል ብላ ነው
‹‹እንዴ ንስር የሞተ ነገር እንደማይነካ አታውቂም…››
‹‹አላውቅም››አለች
‹‹እኔም አላውቅም ››በማለት ድጋፍ ሰጣት ኤልያስ
ማብራሪያዬን በኩራት ቀጠልኩ ‹‹ንስር ኩሩ ነው…እራሱ አባሮ… እራሱ ታግሎ …እራሱ ገድሎ ካልሆነ ነክች አያደርግም…ለማንኛውም አሁን ተዘጋጂ ቁጭ በይ ››….ቁጭ አለች…
‹‹ይሄሁልሽ አሁን ንስሬ ያግዘኝና ከአባትሽ መንፈስ ጋር አገናኝሻለሁ...ማለት የእኔን አንደበት ተጠቅመው አባትሽ ቀጥታ ያናግሩሻል..በእኔ አንደበት በራሳቸው ድምፅ››
‹‹እሺ››
‹‹ኤርምያስ አንተ ደግሞ ካለህበት እንዳትነቃነቅ..ምንም የሚረብሽ ነገር ካለ ትኩረቴን ስለሚበታን መሀል ላይ ግንኙነቱ ሊቋረጥ ይችላል››
‹‹አረ በፍጽም ይሄው ንቅንቅ አልልም..ትንፋሼ እራሱ አይሰማም››አለና በተቀመጠበት ጭብጥብጥ አለ
ሁሉም ነገር ዝግጁ መሆኑን ሳታረጋግጥ አዕምሮዋን ከንሰሯ ጋር አገናኘቸው..ለደቂቃዎች ተመሰጠች …ይሄን ነገር ከዚህ በፊት አድርጋው አታውቅም ‹‹..ግን ማድረግ አያቅተኝም›ስትል በራሷ ተማመነች….አዎ ንስሯ የአባቷን ነፍስ ካለችበት እንድትመጠ እየጋበዘ ነው..ወይ ብዙም አላስቸገራትም ….ቀጥታ አባትዬው በኬድሮን አንደበት ልጃቸውን ማናገር ጀመሩ……
‹‹ልጄ ሰላሜ…››
ባለማመን መለሰች‹‹ወይ አባዬ..››ተንደርድራ ሬሳውን እያየች
‹‹እዛ ለምን ትፍልጊኛለሽ….…?አይ ልጄ ስጋዬ ውስጥ አይደለሁም.. …ግን ደግሞ ወደዘላለም ማረፊያዬም መሄድ አልቻልኩም..ከሁለቱም ሳልሆን በአየር ላይ ተንጠልጥዬ አለሁልሽ፡፡
‹‹ምነው አባዬ……? እኔ ልሰቃይልህ…..እኔ በአየር ላይ ለዘላለም ተንጠልጥዬ ልቅር››
‹‹አይ ለምን ልጄ…? ለምን..…?ለአንቺማ ይሄ አይገባም…ትቼሽ ስለሄድኩ ይቅርታ ልጄ..ምን ላድርግ የአማላክ ጥሪ ነው….እባክሽ ልጄ ከዚህ በላይ እንድሰቃይ አታድርጊኝ…››
‹‹እንዴ አባዬ እኔ አንተን ማሰቃየት…?››
‹‹አዎ እናቴ… እዚህ እቤቴ ውስጥ በድን አካሌን ታቅፈሽ እንደዚህ ሆነሽ እንዴት እፎይ ብዬ ወደዘላለም የሚወስደኝን መንገዴን እቀጥላለሁ..…?አልችልም ልጄ ..አካሌ መሬት ሳይገባ ነፍሴ ወደአምላኮ ልትሄድ ይከብዳታል..ልጄ እባክሽ በአምላክ ስራ ጣልቃ አትግቢ..››
‹‹እንዴት አባ……? እንዴት ጣልቃ ገባሁ……?.››
‹‹እንዴ ሞትን የፈጠረውን አምላክ እኮ እየተቃወምሽው ነው..ተሳስተሀል እያልሺው ነው››
‹‹አዎ ተሳስቷልማ..እንዴት አንድ አባቴን ይነጥቀኛል..…?እንዴት ባዶዬን ያስቀረኛል….…?.››
‹‹አየሽ ልጄ …ሞት እርግጥ በጥፋታችን ምክንያት የተሸለምነው ቅጣታችን ነው…ይሁን እና በዚህ ምድር ለመኖር እስከመጣን ድረስ ሞታችንም በጣም አስፈላጊ ነው..››
‹‹እንዴት አባ .. …?ሞት ደግሞ እንዴት ነው ጠቃሚ የሚሆነው.?››
እግዜር ፈጥሮ ምድር ላይ ቢረሳንስ ምን ይውጠናል….…?አርጅተን መንቀሳቀስ አቅቶን እቤት እስክንቀር…. ቆዳችን እስኪጨማደድ እና ወበታችን እስኪረግፍ ድረስ አልወስዳችሁም ቢለን ማነው የሚጎዳው……?.ጥርሳችን ረግፎ ገንፎ እንኳን ማኘክ እስኪያቅተን ቢተወን …አይናችን ለግሞ የልጅ ልጆቻችንን ከጎረቤቶቻችን ልጆች መለየት እስኪያቅተን ..መኝታ ቤታችን ከሽንት ቤታችን መለየት እስኪሳነን ድረስ ኑሩ ብንባል ሽልማት ነው ቅጣት…ዕርግማን ነው ምርቃት…?››
‹‹እንዴ አባዬ.. …!!!አንተ እኮ ገና ነህ …ሰባ አመት እንኳን አልሆነህም..…?››
‹‹እኮ እግዚያብሄር ይወደኛል ማለት ነዋ..…?ምላሴ ጣዕም መለየት ሳይሳነው፤አይኖቼ ማንበብ ሳያቆሙ ፤እግሮቼ ላምሸው ከዘራ ሳልይዘ አስታወሶኛል…››
‹‹ግን እኮ አባ እኔን ጥለህ ነው የሄድከው…?››
‹‹የሞት መጥፎው ክፍል ያ ነው….አዎ ሁልግዜ የሆነ ነገር ጥለሽ መሄድሽ አይቀርም…ማንም ቢሆን ከዚህ ምድር ሲሰናበት የሆነ ነገር በጅምር ጥሎ መሄዱ የሆነ የሚወደውን ሰው ሳይሰናበት ማምለጡ ያለ እና ግዳጅም ነው….እና ልጄ አንቺ አፈር ካላቀመሺኝ እና በሀዘን መቆራመድሽን እስካላቆምሽ ድረስ ጉዞዬን መጀመር አልችልም… ብጀምርም ቶሎ አልደርስም..ሀዘንሸ ወደኃላ ይስበኛል….ለቅሶሽ መንገዴን እያጨቀየው ያዳልጠኝ እና አላላውስ ይለኛል…..››
‹‹አባ አረ እኔ እንዲህ የበደልኩህ አልመሰለኝም…?››
‹‹በደልሺኝ እኮ አላልኩም.. ግን በቃ..አንዳንዴ መሆን ያለበት ነገር እንዲሆን መተው ነው..ታግለሽ ልታሸኝፊው ከማትችይው ነገር ጋር መታገል ከድካም ውጭ እርባን ያለው ውጤት አያስገኝም ››
‹‹እና ምን ላድርግ አባ…?››
👍89❤10🥰3👎1🔥1😁1
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ቫይብሬት ላይ የተደረገ ሞባይል ስልክ ላይ ሲደወል እንዳለ ንዝረት ተንቀጠቀጥችና አዕምሮዋን ከንስሯ ጋር አላቀቀች…
ሰላም ወደኬድሮን ተንደርድራ መጥታ እግሯ ሰር ድፍት አለችና‹‹በጣም አመሰግናለሁ….እግዜር ይስጥሽ››
‹‹ተነሺ ..እኔን አታመስግኚ…እሱ በጣም ስለለመነኝ ነው እንዲህ ያደረኩልሽ…››አለቻት
‹‹ኤርሚ እግዜር ይስጥልኝ….አንተንም በጣም ነው የማመስግንህ..ምን አይነት ሰላም በውስጤ እንደተሰራጨ አትገምትም››አለች ወደመቀመጫዋ ተመልሳ በመቀመጥ
‹‹በነጋራችን ላይ በጣም ነው የሚያፈቅርሽ …እንደነገረኝ ከሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ አንቺን ሲያፈቅርሽ ነው የኖረው….አንድም ቀን አንቺን ማፍቀር አቁሞ አያውቅም..ግን በኑሮ ደራጃ ስለምትለያዩ እሺ አትለኝም የሚል ፍራቻ በውስጡ ስላለ ካንቺ ሲሸሽ ነው የኖረው››አፈረጠችለት
ባለማመን አንዴ ኬድሮንን አንዴ እሱን በማፈራረቅ ማየት ጀመረች..ኤርምያስም የተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ወደወለሉ እንደደፋ ሚገባበት ጠፍቶታል እጆቹን እያፍተለተለ ነው…
‹‹አላውቅም ነበር…ኤርምያስ እኔን ማፍቀር….…?››
‹‹አዎ….ኤርምያስ አንቺን…››
‹‹እሺ ጥሩ ነው…አሁን ምን እናደርግ …ኤርሚ እርዳኝ ለእድር ሰዎች ንገራቸው…አባቴ ዛሬውኑ እንዲቀበር እፈልጋለሁ….››
‹‹አረ እሺ… ችግር የለውም… አሁኑኑ ነግሬያቸው ልምጣ …ስልካቸውን ስለማላውቅ እናቴ ጋር ሂጄ …››ብሎ ተነሳ
ኬድሮን የተለየ ሀሳብ አመጣች‹‹ቆይ መጀመሪያ የሬሳ ሳጥን እንግዛና አባትሽኝ በሳጥኑ ውስጥ በማድረግ ማዘጋጀት አለመብን..አሁን ዕድርተኛው መጥተው ጓደኞቸው ተሰብስበው እንገንዝ ማለታቸው አይቀርም …እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሌላ ሀሚት ላይ ይጥልሻል…በህግም ሊያስጠረጥርሽ ይችላል››
‹‹ታዲያ ምን እናድርግ››አለች ግራ ገብቷትና ያለሳበችውን ነገር ስላነሳው ደንግጣ
‹‹ግድ የለም እኔና ኤርሚ ሳጥኑን ይዘን እንምጣ..ሁሉንም ከጨረስን ብኃላ ለሌላው ሰው እንናገራለን….››
‹‹አስቸገርኮችሁ አይደል…?››
‹አረ አትጨነቂ …እኔን እንደእህትሽ ቁጠሪኝ… ኤሪሚም ያው ያንቺው ነው..››አለችና ምትናገረው ጠፍቷት በመቁለጭለጨ ላይ ሳለች የደነዘዘውን ኤርሚያስን ይዛው ወጣች…
መኪናው ውስጥ ገብተን የሬሳ ሳጥን ወደሚሸጥበት ቦታ እያመሩ ሳለ…
‹‹ምን አይነት ተአምር ነው ያደረግሽው……?.››ሲል ጠየቀት
‹‹ያው ላንተ ስል ነው››
‹‹በጣም ነው የማመሰግንሽ….ግን እንደማፈቅራት ለእሷ ባትነግሪያት ጥሩ ነበር››
‹‹ለምን…?››
‹‹ያው አንደኛ መንገሩ ምንም ውጤት አይኖረውም ሁለተኛ እኔ እና አንቺ……››
‹‹አይ እኔና አንቺ የሚባል ነገር የለም…አኔን እርሳኝ…እኔ ሁለት ቀን ብቻ ነው የቀረኝ..››
‹‹ምን ለመሆን…?››
‹‹ለመብረር…››
‹‹እንዴ የት አሜሪካ ወይስ አውሮፓ……?››
‹‹በለው ከሁለት አንዱ….ስለዚህ እሷኑ ጠበቅ አድርግ.ደግሞ በትክክል ይሳካልሀል….
እንደምታፈቅራት ስነግራት የልቧን ምት በደንብ ታዝቤያለሁ. ዋናው ከዚህ ሀዘን እስክትወጣ ከስሯ አትለይ …….
‹‹እንዴ ወዴት ነው የምለየው….ከእሷ የሚበልጥ ምን ሌላ ጉዳይ ይኖረኛል››
‹‹ምንም ››
‹‹አንቺ ልትበሪ መሆንሽን መስማቴ ግን ቅር አሰኝቶኛል››
‹‹እኔን እርሳኝ አልኩህ እኮ››
‹‹እኮ እንዴት አድርጌ ልርሳሽ…?››
/////
የሰላምን አባት የቀብር ሁኔታ ካመቻቸችና ከተጠናቀቀ በኃላ ሁለቱንም አንድ ላይ ከለቀስተኞች ጋር ጥላቸው እናም በውስጧ ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናብታቸው መልካሙን ሁሉ እየተመኘችላቸው ወደቤቷ ነው የተመለሰችው…ድክምክም ብሏት ነበር…ግቢውን አስከፍታ ስትገባ ግን ድካሟን ሁሉ ከላዮ የሚያበንላት አስደሳች ሁኔታ ነው የጠበቃት…
ግቢው መሀል ላይ ባለች ክፍት ቦታ ጠራጴዛ እና ወንበር ወጥቷል፤…ጠረጵዛው በልዩ ሌዩ ምግቦችና መጠጦች ተሞልቷል …ከዛ አልፎ ዙሪያው በየጥጋጥጉና በየቦታው የዛፍ ቅርንጫፎች ላይም ሳይቀር የተለያዩ የምግብና የፍራፍሬ አይነቶች ተቀምጠዋል…የተለያዩ ጥራጥሬዋች በየቦታው ተበትኗል….በጊቤዋ ውስጥ ያሉ እንስሳት ብቻ ሳይሆኑ እንግዳ የሆኑ ወፎች ሳይቀሩ ግቢውን ወረውት የተበተነላቸውን ጥራጥሬ በደስታ ይለቅማሉ… ጦጣና ዝንጆሮዎቾም ሙዙን እየላጡ ይውጣሉ …የማይፈነጭ እና የማያስካካ ፍጥረት በግቢው አይታይም.. የሆነ እንስሳት አግብቶ ሌሎቹ ሠርግ ተጠርተው አሼሼ ገዳሜ ላይ ያሉ ነው የሚመስለው….ሌላው ይቅር እያንዳንዱ ተክል ስሩ ተኮትኩቶና አፈር ታቅፎ ውሃ ጠግቦ እስኪተፋ ድረስ ጠጥቶ ይታያል….በቃ በግቢው አንድም ያልተደሰተ ፍጥረት አልነበረም..ይሄ ሁሉ በፕሮፌሰሩ የተደረገው እነሱ በተደሰቱበት መጠን እኔ እንደምደሰት በደንብ ስለሚያውቁ ነው፡፡
‹‹አትመጪም… ይሆን ብዬ በስጋት ላይ ነበርኩ …እንኳን በሰላም መጣሽ››አሏት ከእድሜ ጫና የተነሳ ያጎበደድት ፕሮፌሰር…
‹‹አይ እፈልግሻለሁ ብለውኝ የለ..…….?በዛ ላይ አንድ ቀን ብቻ ነው የቀረኝ …ማታ ወደ እናቴ እሄዳለሁ.አዎ ነገ ሙሉውን ቀን ከእሷዋ ጋር ነው ማሳለፍ የምትፈልገው………››
‹‹ጥሩ ጥሩ..ነይ እዚህ ጋር ቁጭ በይ›› ብለው ምግብ በሞላበት ጠረጴዛ ዙርያ ከበው ከተቀመጡ ወንበሮች ውስጥ አንድን ሳቡላት… አመስግና ተቀመጠች፡፡
የእጅ ውሀ አመጡላት …‹‹አረ እራሴ እታጠባለሁ›› ብላ በራሷ ተጣበች… ሳሀን ስባ ምንም እንኳን የምግብ ፍላጎት ባይኖራትም እሷቸውን ለማስደሰት ስትል ብቻ መብላት ጀመረች… እሳቸውም ከፊት ለፊቷ ተቀምጠው በስስት እያዮት መመገብ ጀመሩ…
‹‹የሚጠጣ ምን ልቅዳልሽ…….?››
‹‹ውሀ ››
‹‹ወይን ወይም ሌላ ነገር አይሻልሽም…….?››ካለወትሮዋ ዉሀ ማለቷ አስገርሞታል
‹‹አይ ውሀ ነው የምፈልገው….››
‹‹እሺ ካልሽ ››ብለው ውሀ ቀዱላት፡፡
‹‹ጋሼ በዚህ ምድር በኖርኩበት ዓመት የተረዳሁት ነገር ቢኖር ምድር መተኪያ የሌላቸው ሁለት ነገሮች መታዳሏን ነው ….አዎ እናትና ውሃ የዚህ ዓለም ሁለት ልዩዎች ናቸው…››
‹‹እንዴት ልጄ..…….?እንዴት እንደዛ ተረዳሽ…?››
‹‹እናታችን መጀመሪያ ገነታችን ነች..ከተፈጠርንበት ቀን አንስቶ እስክንወለድበት ቀን ድረስ በእናታችን መሀፀን ውስጥ ገነታዊ ኑሮ ነበር የምነኖረው… ያ ስፍራ ሁሉ ነገር በፍፅምና እንከን አልባ ስፍራ ነበር..ሁላችንም ከዛ ያለፍላጎታችን ተገፍትረን ስንወጣ(ስንወለድ) እሪ ብለን ለቅሶችንን የምንለቀው ምን እንዳጣን በደመነፍስ ስለሚገባን ነው…አዳም እና ሄዋን በሰሩት ሀጥያት ከገነት ወደምድር ተባረሩ የሚባለው ሌላ አይደለም ከእናት መህፀን ወደምድር ተገፍትሮ መውጣት ነው…ከዛ በኋላም ቢሆን እናት ምን ጊዜም እናት እንደሆነች ነው ምትቀጥለው… እንዳላረጀን እና እንዳላበቃልን የሚሰማን እናታችን በሰላሳ አመታችንም እንደ ህፃን ስትቆጣን ስናይ ነው..ጭንቅላታችንን ስትዳብስልን…ተይ አንቺ ልጅ ብርድ ይመታሻል ስትለን ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ቫይብሬት ላይ የተደረገ ሞባይል ስልክ ላይ ሲደወል እንዳለ ንዝረት ተንቀጠቀጥችና አዕምሮዋን ከንስሯ ጋር አላቀቀች…
ሰላም ወደኬድሮን ተንደርድራ መጥታ እግሯ ሰር ድፍት አለችና‹‹በጣም አመሰግናለሁ….እግዜር ይስጥሽ››
‹‹ተነሺ ..እኔን አታመስግኚ…እሱ በጣም ስለለመነኝ ነው እንዲህ ያደረኩልሽ…››አለቻት
‹‹ኤርሚ እግዜር ይስጥልኝ….አንተንም በጣም ነው የማመስግንህ..ምን አይነት ሰላም በውስጤ እንደተሰራጨ አትገምትም››አለች ወደመቀመጫዋ ተመልሳ በመቀመጥ
‹‹በነጋራችን ላይ በጣም ነው የሚያፈቅርሽ …እንደነገረኝ ከሆነ ከልጅነቱ ጀምሮ አንቺን ሲያፈቅርሽ ነው የኖረው….አንድም ቀን አንቺን ማፍቀር አቁሞ አያውቅም..ግን በኑሮ ደራጃ ስለምትለያዩ እሺ አትለኝም የሚል ፍራቻ በውስጡ ስላለ ካንቺ ሲሸሽ ነው የኖረው››አፈረጠችለት
ባለማመን አንዴ ኬድሮንን አንዴ እሱን በማፈራረቅ ማየት ጀመረች..ኤርምያስም የተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ወደወለሉ እንደደፋ ሚገባበት ጠፍቶታል እጆቹን እያፍተለተለ ነው…
‹‹አላውቅም ነበር…ኤርምያስ እኔን ማፍቀር….…?››
‹‹አዎ….ኤርምያስ አንቺን…››
‹‹እሺ ጥሩ ነው…አሁን ምን እናደርግ …ኤርሚ እርዳኝ ለእድር ሰዎች ንገራቸው…አባቴ ዛሬውኑ እንዲቀበር እፈልጋለሁ….››
‹‹አረ እሺ… ችግር የለውም… አሁኑኑ ነግሬያቸው ልምጣ …ስልካቸውን ስለማላውቅ እናቴ ጋር ሂጄ …››ብሎ ተነሳ
ኬድሮን የተለየ ሀሳብ አመጣች‹‹ቆይ መጀመሪያ የሬሳ ሳጥን እንግዛና አባትሽኝ በሳጥኑ ውስጥ በማድረግ ማዘጋጀት አለመብን..አሁን ዕድርተኛው መጥተው ጓደኞቸው ተሰብስበው እንገንዝ ማለታቸው አይቀርም …እንደዛ ከሆነ ደግሞ ሌላ ሀሚት ላይ ይጥልሻል…በህግም ሊያስጠረጥርሽ ይችላል››
‹‹ታዲያ ምን እናድርግ››አለች ግራ ገብቷትና ያለሳበችውን ነገር ስላነሳው ደንግጣ
‹‹ግድ የለም እኔና ኤርሚ ሳጥኑን ይዘን እንምጣ..ሁሉንም ከጨረስን ብኃላ ለሌላው ሰው እንናገራለን….››
‹‹አስቸገርኮችሁ አይደል…?››
‹አረ አትጨነቂ …እኔን እንደእህትሽ ቁጠሪኝ… ኤሪሚም ያው ያንቺው ነው..››አለችና ምትናገረው ጠፍቷት በመቁለጭለጨ ላይ ሳለች የደነዘዘውን ኤርሚያስን ይዛው ወጣች…
መኪናው ውስጥ ገብተን የሬሳ ሳጥን ወደሚሸጥበት ቦታ እያመሩ ሳለ…
‹‹ምን አይነት ተአምር ነው ያደረግሽው……?.››ሲል ጠየቀት
‹‹ያው ላንተ ስል ነው››
‹‹በጣም ነው የማመሰግንሽ….ግን እንደማፈቅራት ለእሷ ባትነግሪያት ጥሩ ነበር››
‹‹ለምን…?››
‹‹ያው አንደኛ መንገሩ ምንም ውጤት አይኖረውም ሁለተኛ እኔ እና አንቺ……››
‹‹አይ እኔና አንቺ የሚባል ነገር የለም…አኔን እርሳኝ…እኔ ሁለት ቀን ብቻ ነው የቀረኝ..››
‹‹ምን ለመሆን…?››
‹‹ለመብረር…››
‹‹እንዴ የት አሜሪካ ወይስ አውሮፓ……?››
‹‹በለው ከሁለት አንዱ….ስለዚህ እሷኑ ጠበቅ አድርግ.ደግሞ በትክክል ይሳካልሀል….
እንደምታፈቅራት ስነግራት የልቧን ምት በደንብ ታዝቤያለሁ. ዋናው ከዚህ ሀዘን እስክትወጣ ከስሯ አትለይ …….
‹‹እንዴ ወዴት ነው የምለየው….ከእሷ የሚበልጥ ምን ሌላ ጉዳይ ይኖረኛል››
‹‹ምንም ››
‹‹አንቺ ልትበሪ መሆንሽን መስማቴ ግን ቅር አሰኝቶኛል››
‹‹እኔን እርሳኝ አልኩህ እኮ››
‹‹እኮ እንዴት አድርጌ ልርሳሽ…?››
/////
የሰላምን አባት የቀብር ሁኔታ ካመቻቸችና ከተጠናቀቀ በኃላ ሁለቱንም አንድ ላይ ከለቀስተኞች ጋር ጥላቸው እናም በውስጧ ለመጨረሻ ጊዜ ተሰናብታቸው መልካሙን ሁሉ እየተመኘችላቸው ወደቤቷ ነው የተመለሰችው…ድክምክም ብሏት ነበር…ግቢውን አስከፍታ ስትገባ ግን ድካሟን ሁሉ ከላዮ የሚያበንላት አስደሳች ሁኔታ ነው የጠበቃት…
ግቢው መሀል ላይ ባለች ክፍት ቦታ ጠራጴዛ እና ወንበር ወጥቷል፤…ጠረጵዛው በልዩ ሌዩ ምግቦችና መጠጦች ተሞልቷል …ከዛ አልፎ ዙሪያው በየጥጋጥጉና በየቦታው የዛፍ ቅርንጫፎች ላይም ሳይቀር የተለያዩ የምግብና የፍራፍሬ አይነቶች ተቀምጠዋል…የተለያዩ ጥራጥሬዋች በየቦታው ተበትኗል….በጊቤዋ ውስጥ ያሉ እንስሳት ብቻ ሳይሆኑ እንግዳ የሆኑ ወፎች ሳይቀሩ ግቢውን ወረውት የተበተነላቸውን ጥራጥሬ በደስታ ይለቅማሉ… ጦጣና ዝንጆሮዎቾም ሙዙን እየላጡ ይውጣሉ …የማይፈነጭ እና የማያስካካ ፍጥረት በግቢው አይታይም.. የሆነ እንስሳት አግብቶ ሌሎቹ ሠርግ ተጠርተው አሼሼ ገዳሜ ላይ ያሉ ነው የሚመስለው….ሌላው ይቅር እያንዳንዱ ተክል ስሩ ተኮትኩቶና አፈር ታቅፎ ውሃ ጠግቦ እስኪተፋ ድረስ ጠጥቶ ይታያል….በቃ በግቢው አንድም ያልተደሰተ ፍጥረት አልነበረም..ይሄ ሁሉ በፕሮፌሰሩ የተደረገው እነሱ በተደሰቱበት መጠን እኔ እንደምደሰት በደንብ ስለሚያውቁ ነው፡፡
‹‹አትመጪም… ይሆን ብዬ በስጋት ላይ ነበርኩ …እንኳን በሰላም መጣሽ››አሏት ከእድሜ ጫና የተነሳ ያጎበደድት ፕሮፌሰር…
‹‹አይ እፈልግሻለሁ ብለውኝ የለ..…….?በዛ ላይ አንድ ቀን ብቻ ነው የቀረኝ …ማታ ወደ እናቴ እሄዳለሁ.አዎ ነገ ሙሉውን ቀን ከእሷዋ ጋር ነው ማሳለፍ የምትፈልገው………››
‹‹ጥሩ ጥሩ..ነይ እዚህ ጋር ቁጭ በይ›› ብለው ምግብ በሞላበት ጠረጴዛ ዙርያ ከበው ከተቀመጡ ወንበሮች ውስጥ አንድን ሳቡላት… አመስግና ተቀመጠች፡፡
የእጅ ውሀ አመጡላት …‹‹አረ እራሴ እታጠባለሁ›› ብላ በራሷ ተጣበች… ሳሀን ስባ ምንም እንኳን የምግብ ፍላጎት ባይኖራትም እሷቸውን ለማስደሰት ስትል ብቻ መብላት ጀመረች… እሳቸውም ከፊት ለፊቷ ተቀምጠው በስስት እያዮት መመገብ ጀመሩ…
‹‹የሚጠጣ ምን ልቅዳልሽ…….?››
‹‹ውሀ ››
‹‹ወይን ወይም ሌላ ነገር አይሻልሽም…….?››ካለወትሮዋ ዉሀ ማለቷ አስገርሞታል
‹‹አይ ውሀ ነው የምፈልገው….››
‹‹እሺ ካልሽ ››ብለው ውሀ ቀዱላት፡፡
‹‹ጋሼ በዚህ ምድር በኖርኩበት ዓመት የተረዳሁት ነገር ቢኖር ምድር መተኪያ የሌላቸው ሁለት ነገሮች መታዳሏን ነው ….አዎ እናትና ውሃ የዚህ ዓለም ሁለት ልዩዎች ናቸው…››
‹‹እንዴት ልጄ..…….?እንዴት እንደዛ ተረዳሽ…?››
‹‹እናታችን መጀመሪያ ገነታችን ነች..ከተፈጠርንበት ቀን አንስቶ እስክንወለድበት ቀን ድረስ በእናታችን መሀፀን ውስጥ ገነታዊ ኑሮ ነበር የምነኖረው… ያ ስፍራ ሁሉ ነገር በፍፅምና እንከን አልባ ስፍራ ነበር..ሁላችንም ከዛ ያለፍላጎታችን ተገፍትረን ስንወጣ(ስንወለድ) እሪ ብለን ለቅሶችንን የምንለቀው ምን እንዳጣን በደመነፍስ ስለሚገባን ነው…አዳም እና ሄዋን በሰሩት ሀጥያት ከገነት ወደምድር ተባረሩ የሚባለው ሌላ አይደለም ከእናት መህፀን ወደምድር ተገፍትሮ መውጣት ነው…ከዛ በኋላም ቢሆን እናት ምን ጊዜም እናት እንደሆነች ነው ምትቀጥለው… እንዳላረጀን እና እንዳላበቃልን የሚሰማን እናታችን በሰላሳ አመታችንም እንደ ህፃን ስትቆጣን ስናይ ነው..ጭንቅላታችንን ስትዳብስልን…ተይ አንቺ ልጅ ብርድ ይመታሻል ስትለን ነው፡፡
👍91❤8👏4😢4🔥2🥰2🤔1