አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
459 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ያልተቋጨ


#ክፍል_ሁለት


#በክፍለማርያም

ወደ ህሊና አመራ ትንሳኤ ከደረጃ እየወረደች ወደሱ ትይዩ እየመጣችዉ ያለችውን ህሊናን ሲያያት ፊቱ እየቀላና ድንብርብሩ እየወጣ በር ላይ እየጠበቀዉ ወዳለዉ ጉዋደኛዉ ጋር ደርሶ
"ባክህ ፈራሁዋት አፍቃሪዉ ምናምን እያልክ ደሞ እንዳትሰድበኝ"
እያለ ቦርሳዉን ከጉዋደኛዉ ተቀብሎ ወደ ቤቱ አመራ።

ቅዳሜ እና እሁድን በጠዋት እየተነሳ ለሰኞ የፍቅር ጥያቄ ለማቅረብ እና እስዋ ፊት ሲደርስ ወንዳወንድ ለመምሰል ፑሽ አፕ ፑል አፕ በተጨማሪም ቤቱ ዉስጥ በስንሚንቶ በሰራዉ ክብደት ስፖርት ሲሰራ ፍርሀቱን ለማስወገድ እንደ እብድ መስታወት ፊት ቆሞ ሲለፈልፍ ሰኞ ደረሰ።

እንደወትሮዉ የህሊና ክፍል ከትንሳኤ ክፍል ቀጥሎ ስለሆነ ባንዲራ ተሰቅሎ ተማሪ ወደየ ክፍሉ ከገባ በኋላ አይኗን ሳያይ መዋል ስለማያስችለዉ ቀስ እያለ እየተራመደ ወደሱ ክፍል ከመግባቱ በፊት የህሊናን ክፍል በር አሻግሮ በአይኑ ህሊናን መፈለግ ጀመረ።
የቀረች መስሎት ሊበሳጭ ነበር ነገር ግን ፊቷን አዙራ ወሬ እያወራች ስለነበር ነዉ።
መጥታለች በርቀት ሲመለከታት ደስ አለዉ ደስታው በምንም የማይተካ ነበር ፈገግ እያለ በልቡ ስላያት ተመስጌን መጥታለች እያለ ወደሱ ክፍል ሲገባ ጉዋደኞቹ በሳቅ ተቀበሉት
ከዮናስ ጎን የተቀመጠዉ እዮብ በትንሳኤ አፍቅሮ እንደዚህ መሆን አይስቅበትም ምን አልባት እሱም ከሌላ ፍቅር ሊኖርበት ይችላል ዮናስም ቢሆን በሀሪዉ ሆኖ የትንሳኤ ሁኔታ ስለሚገርመዉ ይስቅበታል እንጂ ጨክኖበት አልነበረም።
የህሊና ጉዋደኞች እነ ትንሳኤ ክፍል ስላሉ ሁሌ ህሊና ምሳ ለመብላት እነሱጋር ትመጣለች ትንሳኤም መጀመርያ በህሊና ፍቅር የወደቀዉ እሷ ስትመላለስ አይቷት ነዉ
ቀኑን ያስታዉሰዋል ምሳ ስዓት ላይ አሸናፊ የሚባሉ አብሮት አንድ ዴስክ ላይ የሚቀመጥ ተማሪ በስልኩ ሙዚቃ ከፍቶ ነበር
"ለምን አየኝ አለች ሳያት እሷን ብቻ
መዉደዴን ስነግራት አርጋዉ የጥላቻ.."
እያለ የሚቀጥል የመስፍን በቀለን ዘፈን ህሊና ቦርሳ አንግባ በምን እንደምትስቅ ባያዉቅም አነስአነስ ያሉ ነጭ ጥርሶቿን እያሳየች ወደነትንሳኤ ክፍል ገባች።
ወደ ክፍሉ ብቻ አደለም የገባችዉ እንደሙዚቃዉ በልቡ ግጥምና ዜማዋ ሳቋና ሁሉነገሯ ልቡ ዉስጥ ገባ።
ዛሬም ምሳ ስዓት ሲደወል ጉዋደኞቹ
"እንዉጣ"
ቢሉትም በልቡ ያሰበዉ ነገር ስለነበር
"አልወጣም የምፅፈዉ ነገር አለ"
ሲላቸዉ ጉዋደኞቹ ጥለዉት ወጡ
ትንሳኤ ጠዋት ቁርስ በልቶ ከቤቱ ስላልወጣ ሆዱ የርሀብ ጥያቄ እያሰማ ነበር
ህሊና ወደ ጉዋደኞቿ ክፍል ስትገባ ትንሳኤ ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ በረንዳ ወጥቷ በልታ እስክትጨርስ ሠንጎማለል ጀመረ።
እርቦታል ቤቱ ቅርብ ስለነበር ሄዶ መብላት ይችላል ነገር ግን ልቡ ዉስጥ ያለዉን ለመናገር ቻል አርጎ ከአሁን አሁን በልተዉ ጨረሱ እያለ በአይኑም ለማረጋገጥ እያያቸዉ ቆይቶ በልታ ጨርሳ እጇን ታጥባ እንደጨረሰች።
ለመጥራት ፈልጎ እንዴት መጥራት እንዳለበት ግራ ገብቶት ለጉዋደኞቹ እንደለመደዉ በቅርብ እርቀት ላይ ሆና አፉዋጨላት ደፋር ደፋር እያጫወተዉ ነበር።
ህሊና ዞራ እያየችዉ እኔን ነዉ ለማለት ሌባ ጣቷን ወደ ደረቷ አስጠግታ ስታሳየዉ አዎ ለማለት አንገቱን ከላይ ወደታች እየነቀነቀ በእጆቹ ጠራት
"አንዴ መጣሁ"
አለችዉና ወደ ጉዋደኞቿ ተመለሰች
ትንሳኤ ፍርሀት አይን አዉጥቶ ሂድ ሂድ ቢለዉም ቅዳሜና እሁድ የለፋበት ስፖርት ጥቂት ወኔ ሰጥቶት ደረቱን ነፍቶ ጠበቃት አጠገቡ ህሊና
"አቤት"
ብላ ስትጠጋዉ ግን ተንፍሶ ጥቂት ዝም አለና
እጁን እየዘረጋ
"ትንሳኤ"
አላት ስሙን ለመናገር እየፈለገ
"ህሊና"
ብላዉ የሚነግራትን ለመስማት አይን አይኑን አየችዉ
ትንሳኤ አይኗን እያየ በልቡ
"አቤት ሲያምር ደሞ የሆነ የሚያሳዝን ነገር አላት "
ብሎ በድንጋጤ ሊያዋራት አፉን ከፈተ
"ካየሁሽ ቀን ጀምሮ እወድሻለሁ"
የማይባል ነገር አለ
መሸወዱ አመታት አልፎ ነዉ የገባዉ እንዴት አዉርተሀት በደንብ እንኳን አይታህ የማታዉቅ ሴትን እንደዚህ ይባላል

💫ይቀጥላል 💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1👍1
#ያልተቋጨ


#ክፍል_ሶስት


#በክፍለማርያም

...እንዴት ይባላል
ህሊና ደንገጥ ብላ አየችዉ እብድም ሳይመስላይ አይቀርም ፊቷ ላይ የመደንገጥ እና የመገረም የሚመስል ድባብ ይታይባታል ቶሎ ለመራቅ አስባ አፏ ላይ የመጣላትን

"ጉዋደኛ አለኝ"

ብላዉ ጥላዉ ወደ ጉዋደኞቿ ገባች።
የዛን ለት ወድያዉ እሷ ጥላዉ ስትገባ ደብተሩን እንኳን ሳይዝ እየተበሳጨ እየተመናቀረ ከትምህርት ቤቱ ግቢ ወጣ
ግራ የተጋባ ስሜት መናገሩ የልቡን መተንፈሱ ቢቀለዉም የመለሰችለት መልስ ያሳየችዉ ፊት ግን አስከፍቶታል
አፍቃሪ የሚጠብቀዉ እንደልቡ ፍላጎት ህልሙ ተሳክቶ ማየት ነዉ
ህይወት ግን ወጥንቅጧ የበዛ ስለሆነ አንዳንዴ በአንድ ወገን ያለ ፍቅር ለብቻዉ እንደሻማ በርቶ ይቀልጣል እንጂ አይሰምርም
መንገድ ላይ እየተሪመደ አንድ መንገድ ዳር የተቀመጠ ሲጋራ የሚያጨስ ከትንሳኤ እድሜ የሚበልጥ ልጅ
"ና" ብሎ ጠራዉ
ትንሳኤ እየተወዛገበ

"አቤት" እያለ ተጠጋዉ
"ስንት ብር ይዘሀል "
እያለ ልጁ ቆመ
ትንሳኤ ለራሱ ከባድ የፍቅር ረመጥ ዉስጥ ነዉ አደለም የማንም ጉልበተኛ ነኝ ባይ
"ና ያለህን አምጣ" ብሎት
ትንሳኤ ሳያንገራግር ወደ ልጁ ቦክስ ሰደደ ልጁም ወደ ትንሳኤ የመልስ ምት ላከ ገላጋይ ባይገባ ሁለቱም ይጎዳዱ ነበር። ትንሳኤን ሲያገላግሉ የያዙት ሰወች
"ምን አይነት ልብ ነዉ ያለህ ከታላቅህ ጋር ትጣላለህ"
እያሉ ሲመክለሩት የልብ ልብ ተሰምቶት ድጋሜ ካልተጣላሁ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ቢልም ጉልቤ ለመሆን የሞከረዉ ልጅ ግረግሩ እና የትንሳኤ ፉከራ ስላልጣመዉ ከአካባቢዉ ተሰወረ።

በነጋታዉ ትንሳኤ ወደ ክፍል እንደገባ ዮናስ በፈገግታ ተቀበለዉ
"ጀግናችን ወሬ አይደበቅም ስታዋራት ሰው አይቶካል ምን ተፈጠረ ጭዌዉን እንደወረደ"
ሲለዉ ሌሎች ጉዋደኞቹም በተሰበሰቡበት ትንሳኤ የተፈጠረዉን በሙሉ ነገራቸዉ ዮናስ ተበሳጨ
"አረ አፍቃሪዉ ተበልተሀል የሆነ በሙድ አትገባላትም ነበር ዝም ብለህ እወድሻለሁ አረ አይነፌክስ"
ትንሳኤ ላይ የእዉነት ወረደበት ተናዶ
ለትንሳኤ መልካም ስለሚያስብ ነበር
ምክንያቱም ሲጨነቅ ስለሷ ሲያስብ የእዉነት እንደወደዳት አስተዉሎታል
ትንሳኤም ግልፅ ስለሚያወራ ቀንም ማታም ስለሷ ቢያወራ ስለማይጠግብ ሁሉንም ስሜቱን ሳይደብቅ ይነግራቸዉ ስለነበረ ነዉ
በተቃራኒዉ እዮብ
"ዋናዉ ማዋራትህ ነዉ አንበሳ እኔኮ ትመቺኛለሽ"
ሲል በእጁ የትንሳኤን ትከሻ ከነካ በኃላ
"በቅርቡ የሆነ ብር አገኛለሁ እጋብዝሀለዉ ጭንቀትህንም ትረሳለህ"
ሲል አከለበት
ታሪኩ እንዲህ እያለ ቀጠለ ትንሳኤ እወድሻለሁ ካላት በኋላ ህሊና ገና ከሩቁ ትንሳኤን ካየችዉ መሸሽ መንገድ መቀየር በተለይ የትንሳኤ ክፍል ካሉት ጉዋደኞቿ ጋር ትንሳኤን ላለማየት እሱ ክፍል መምጣት ተወች
በተለይ የጉዋደኞቿ አይን ትንሳኤ ላይ በረታበት በአይናቸዉ ያወራሉ ሁሌ ሲያያቸወ እያሽሟጠጡበት እየተረቡት ይመስለዋል አንዳንዴ ወንድ ቢሆኑና ብደባደባቸዉ ብሎ ያስባል
በአይናቸዉ ጥንብእርኩሱን ያወጡት ጀመር።

ህሊናም ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ተጠየፈችዉ ትሸሸዉ ጀመር
ትንሳኤ ፍቅር ብሎ የጉዋደኛዉን የዮናስን ምክር ሳይሰማ ዘባርቆ የተምታታ ስሜት ዉስጥ ገብቶ
በተቀመጠበት ስዓት እዮብ
"ፈታ ላርግህ ወንድሜ"
ብሎ ይዞት ከትምህርት ቤቱ ግቢ ምሳ ሰአት ላይ ይዞት ወጣ
በአቅራቢያቸዉ ካለ ጠላ ቤት ገብተዉ የሚጣፍጥ ድንች በሚጥሚጣ ከበሉ በኋላ ጠላ በጣሳ ይዘዉ እየጠጡ ተቀመጡ
ትንሳኤ ስለ ህሊና መለዋወጥ በልቡ እያሰበ ጠላዉን መጎንጨት ተያያዘዉ ወደ ሞቅታ ሲገባ ተነስቶ ቆሞ
የለበሰዉን የትምህርት ቤቱን ሸሚዝ አዉልቆ በቲሸርት ሆኖ ወደ ትምህርት ቤቱ በፍጥነት መራመድ ጀመረ
ሁኔታዉ ያልጣመው እዮብ ሂሳብ ከፍሎ እየሮጠ ተከተለው
ትንሳኤ ደረጃ ወጥቶ ወደ ህሊና ክፍል ሊደርስ ሲል አፍንጫዉን ነካ አርጎ አየር ከሳበ በኋላ
ወደ ህሊና ክፍል ስትት ብሎ ገባ

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍1
#ያልተቋጨ


#ክፍል_አራት


#በክፍለማርያም

...ስተት ብሎ ገባ ህሊና ጥግ ላይ ወሬ እያወራች ነበር ስታየዉ በትንሹ ደንገጥ ብላ አፈጠጠችበት
ትንሳኤ ፊት ለፊቷ ቆሞ እጁን ወደ ኋላ ማረጉን ሲያስተዉል አሁን የመጣሁት ልለምናት እንዳይመስላት አለና እጆቹን አፍታቶ የእስዋ ዴስክን አሰደግፏቸዉ ጎንበስ ብሎ ቆመ
ህሊና ምን ሆኖ ነዉ እያለች በመገረም ታየዋለች

"ምን ሆነሽ ነዉ ግን"
አላት ቆጣ ብሎ

"ምን ሆንኩ"

አለችዉ ለስለስ ባለ ዜማ ባለዉ አነጋገር
ትንሳኤ ለአፍታ የጎዋደኞቿ ግልምጫ የእሷ መደባበቅ የእሱ የፍቅር ጥያቄ አለመሳካት ከጠጣዉ መጠጥ ጋር ተደራርቦ
"የወደድኩሽ መስሎሽ ነዉ እንደዚህ የሚያረግሽ አልወድሽም እሺ አልወድሽም"
ጮክ ብሎ ተናገረ ጉዋደኛዉ እዮብ ደርሶ እንዳይመታት ይሄ እብድ እያለ ይዞት ሊወጣ ሲሞክር
ትንሳኤ አስቸገረ አፉ
"አልወድሽም አልወድሽም "
ይበልእንጂ አሁንም ልቡ ዉስጥ ናት
ህሊና ምን ነካዉ በሚል አስተያየት እያየችዉ ትንሳኤ በጉዋደኛዉ እየተጎተተ ወጣ።
ከዛን ቡሀላ ህሊና ጭራሽ ከአይኑም እየራቀች መጣች
ሁሌ ሲገባ ግን በእሷ ክፍል እያለፈ አንገቱን ሰገግ አርግ በአይኖቹ ሳይፈልጋት ክፍሉ አይገባም
የጉዋደኞቿም አይን አፈር ከመሬት የሚያበላ ነበር
በዛ ሁሉ መሀል ግን ጉዋደኞቹ ሲያስባት እና ሲያስታዉሳት በቀልድ እያሳቁ እያስረሱት በተለይ ጠጥቶ
"አልወድሽም አልወድሽም"
ብሎ የጮሀዉን እያነሱ እሱንም ሲያፅናኑት በአይን ብቻ ጠዋት እና ከትምህርት ቤት ሲለቀቁ ስትወጣ ተደብቆ እያያት አመቱ አልቆ ክረምት ሲገባ በልቡ ብቻ ይዞ እያሰባት ተቀመጠ
በዛን ክረምት ትንሳኤ ብዙ አይነት መፅሀፍቶችን ሲያነብ ከጉዋደኞቹም ጋር ሲያዝግ ከሴቶች ጋር መቀራረብ መነጋገር የመሳሰሉት ፍርሀቶቹ ዘበት ሆነዉ ጠፍተዉ
በሚቀጥለዉ አመት ትምህርት ሲጀምሩ ምላስ አርዝሞ ከትምህርቱ ቀንሶ ሌላ ሰዉ ሆኖ ገባ
ያልተቀየረዉ የህሊና ፍቅር ግን አሁንም ልቡ ዉስጥ ነበር ትምህርት ቤት ውስጥ መጀመርያ ከህሊና ጋር ሲተያዩ በረንዳ ላይ ቆማ ነበር
እንዳያት ደስ አለዉ ፈገግ እያለ ተጠጋትና
"እዚህ ምን ትሰርያለሽ ገብተሽ አትማሪም"
አላት ህሊና አይኖቿን ወደ ላይ አርጋ
"ምን አገባህ"
አለችዉ
"ዋ ስትፎርፊ እንዳላይሽ"
እያለ ቆመዉ ወደሚጠብቁት ጉዋደኞቹ አመራ።
የሆነቀን ምሳ ሰአት ናፍቃዉ ወደሷ ክፍል አመራ
አሁንም ቢሆን ግን ከሌላ ሴት ልጅ ጋር ሲሆን እንደሚያወራዉ ከበፊቱ ፍርሀቱ ቀንሷል እንጂ እሷ ጋር ሲደርስ ቃላት ይጠፉበታል ሲገባ ነጭ ወረቀት ላይ ስዕል እየሳለች አገኛት
"ቆይ እኔ ልሳልልሽ"
እያለ እስራሱን ከእሷ እጅ ተቀበላት ከጎኗ ያሉት ገዋደኞቿ እሷ እርሳሱን ለማስመለስ ስትሞክር እያዩ ይስቃሉ
ትንሳኤ በቆመበት ሳያስበዉ አፍንጫውን ሲነካ የደረቀ ን ጥ ከአፍንጫዉ ወድቆ ወረቀቱ ላይ አረፈ ህሊና
"እእይይይይይ"
እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ።
ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
👍1
#ያልተቋጨ

#ክፍል_አምስት (የመጨረሻ ክፍል)

#በክፍለማርያም

ህሊና
"አይይይይይይይ" እያለች ወረቀቱን አራገፈችዉ ትንሳኤ ጀርባዉን ሲያልበዉ ይታወቀዋል
ከአጠገቧ ገፋ አርጓት አይኑን በጨዉ አጥቦ ተቀመጠ
አንዳንዴ ተዋረድ ካለህ እንደዚህ ነዉ
አጠገቧ ተቀምጦ እጆቹን ወደ ሰደርያዋ ኪስ በቀስታ ሰዶ ከኪሷ ሶፍት አወጣ
አንደኛዋ ጉዋደኛዋ አይታዉ ሳቀች ህሊናም እንደወሰደባት ስታዉቅ ተናዳ አፈጠጠችበት
ትንሳኤም በሶፍቱ አፍንጫዉን እያበሰ በመዋረዱ በልቡ በጣም እያዘነ ሲወጣ በር ላይ ዮናስ ጠበቀዉ

"ባክህ ተዋረድኩልህ"

አለዉ ትንሳኤ በንዴት ከንፈሩን ነክሶ
"ምን ተፈጠረ"
ሲል ዮናስ አፋጠጠዉ
"ደረቅ መሆኑ ጠቅሞኛል ...."
እያለ ትንሳኤ የተፈጠረዉን ነገረዉ ከዛን ቀን ጀምሮ ነገሮች በህሊናና በእሱ መሀል ሴጣን እንዳለ ተገነዘበ እየወደዳት እያፈቀራትም ቢሆን ሌላ ሌላ ነገር ዉስጥ ገባ
የሆነ ቀን ሲያገረሽበት ለጉዋደኛዉ
"ጥራልኝ ላዋራት ናፈቀችኝ"
አለዉ
"ምን ጣጣ አለዉ"
ተከተለኝ አለዉና ወደ ህሊና ክፍል አምርተዉ ትንሳኤ በረንዳ ሲቆም ደፋሩ ጉዋደኛዉ ህሊናን አቀፍ አርጎ እያዋራት ይዧት ከወጣ በኋላ
"ተነጋገሩ "
ብሏቸዉ ትንሳኤን እና ህሊናን አገናኝቷቸዉ ሄደ።
"የመጀመርያ ቀን ቦርሳ በትከሻሽ ይዘሽ እየሳቅሽ ስትገቢ ነዉ ያየሁሽ
ደሞ በግራ እጅሽ ነዉ የምትፅፊዉ አደል"
ትንሳኤ ሊያዋራት የመጣዉ ሌላ ቢሆንም የልቡን በቻለዉ ቋንቋ መናገር ቀጠለ
ነገር ግን የህሊና መልስ
"ጉዋደኛ አለኝ አንደዉም አሁን እራሱ ሰዉ አይቶኝ ካንተ ጋር መቆሜን እንዳይነግሩት"
አለችዉ
ሀሳቡ ተበታተነ እኔ ነኝ እንጂ እስዋ አትወደኝም ሲል አስቦ በልቡ እሳት እየነደደ ዉስጡ በንዴት ግሎ
"እሺ ስታገኚኝ ግን አትዝጊኝ ሰላምታ እንኳን"
"እሺ"
ብላዉ ጥላዉ ገባች
ነገር ግን አንዴ ታክሲ ስትጠብቅ ከሩቅ አይቷት በደስታ ክንፍ ብሎ ሲጠጋት እየገላመጠች እራቀችዉ
ተከትሏት ጥቂት ለማዋራት እየሞከረ ተከተላት ነገር ግን እሷ ማዋራት አልፈለገችም
ትንሳኤ አመታት አልፈዉም አሁንም እንደ መጀመርያዉ ቦርሳ ይዛ እየሳቀች ስትገባ ያለዉ ምስል አይምሮዉ ዉስጥ አለ ፍቅሯ አመታት አልፎ እንደ ትላንት ይታወሰዋል መልኳ አይኗ ሰዉነቷ አወራሯ ሁሉ ነገሯ አይረሳዉም
ማፍቀር ማለት የማያገኙትን ሰዉ በተስፋ እንደመጠበቅ ነዉ ስሜቱ ያማል ያስከፋል መንገዱ ዉስጥ ግን አይረሴ ታሪኮች አሉ
አንድ ቀን አጊንቷት ያለ ፍርሀት ያለ ሰቀቀን እንደ ጉዋደኛ እንኳን ቢያዋራት ህልሙ ነዉ አንዳንዶች ለቀልድ ተዋዉቀዉ ይጋባሉ አንዳንዶች የእዉነት አፍቅረዉ ያጣሉ አለም ትገርማለች ፍቅርም ይገርማል ይሄ ታሪክ ለትንሳኤ የህይወቱ ክፍል ለህሊና ተራ ወሬ ሊሆን ይችላል
ትንሳኤ በልቡ የያዘዉ ታሪክ ነዉ ህሊና የናቀችዉ ተራ ነገር
ትንሳኤ በህሊና መፍረድ አቁሟል ምክንያቱም ሰዉ የፍላጎቱ ዉጤት ነዉ
የእሷ ምርጫና ፍላጎት የራሷ ዉሳኔ ነዉ

💫አለቀ💫

ነገ በተለመደው ሰዓት #ህመም_ያዘለ_ፍቅርን #ምእራፍ_ሁለት እንጀምራለን እሰከዛው መልካም ቆይታ🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅርን


#ምእራፍ_ሁለት


#ክፍል_አንድ

#በክፍለማርያም

ፀሀይዋ ለመጥለቅ ጥቂት ሰዐታት ይቀራታል እስዋን እየተመለከቱ ብዛት ያላቸዉ ወንዶች ግቢዉ ዉስጥ ከወዲህ ወድያ ይንጎማለላሉ።

ፍፁም በብቸኝነት ተቆራምቶ ከተቀመጠበት ጥግ ተነስቶ ቆመና ወደ ሰፊዉ ክፍል አምርቶ ወረቀት እና እስኪርቢቶ አንስቶ መፃፍ ጀመረ።
ለመጀመርያ ጊዜ ቤዛዊትን ያገኛት ቀን ሰአት ጠይቃዉ ስትሰድበዉ ታሪኩን እየፃፈ ከታሰረ ለመጀመርያ ጊዜ ፊቱ ላይ ፈገግታ ተነበበ መፃፉን አላቋረጠም የሚያስታዉሳቸዉን የእሱን እና የቤዛዊትን ታሪክ ወረቀቱ ላይ እየከተበዉ ነዉ።
ትምህርት ቤት ዉስጥ የጠቀሰችዉን ሲያስታዉስ ድምፅ አዉጥቶ መንከትከት ጀመረ ከጎኑ የነበሩት እስረኞች እየገላመጡት ከአጠገቡ ተነስተዉ እራቁት ማንም ሰዉ ያንተን ህመም እንዳንተ አያመዉም
ማንም ሰዉ አንተ ያሳለፍከዉ ከባድ ነገር ለእሱ ክብደቱ አይታወቀዉም
መሸከም ስትችል ተቋቁመሀዉ ስታልፍ ያበረታሀል እንጂ አቅቶህ ስትወድቅ የሚያነሳህ ውስን ነዉ።

መፃፉን እየቀጠለ ነዉ ቤዛዊት ፅፋ የምትሰጠዉን ወረቀቶች አሁንም ድረስ ያስታዉሳቸዋል
ህመሟን እብደቷን ሳያዉቅ ቀሚስሽ አጥሯል ሲላት ጠልፎ የሚጥል እረጅም ቀሚስ ለብሳ ቤቱ የመጣችዉንም አልረሳዉም አሁንም እንደታመመች አዉቆ ስላልተዋት ስላልራቃት በራሱ ደስተኛ ነዉ።

ቤዛዊትን ሲያስብ ፈገግታዋ የፊቷ እንቅስቃሴ አይኑ ላይ ይታየዋል ሳቋ በጆሮወቹ ዛሬም ያስተጋባሉ
ንዴትዋን ኩርፊያዋን ህመሟን ሲያስብ ብታናድደዉም ስለተላመዳቸዉ እንደ እንከኖቿም አይቆጥርባትም
የእሱን በድንገት በአጋጣሚ ፍቃዱ የሚባልን የተረገመን ፍጥረት በንዴት ተገፋፍቶ መግደሉን ሲያስብ ፀፀት መላ ሰዉነቱን እየወረረዉ የጀመረዉን ፅሁፍ አቁዋርጦ ማልቀስ ጀመረ።

ፍፁም እስር አልተመቸዉም ለነገሩ መታሰር ለማን ይመቻል ገና አሁን ወዳለበት የእስር ግቢ እንደገባ የሬሽን መዝገብ ዉስጥ ስሙ ስላልተካተተ ደረቅ ዳቦ ብቻ ቀምሶ ትራስ እያስፈለገዉ
ፍራሽ ላይ ጋደም አለ ለማሰብ ግዜ አላገኘም እራሱን ሀይለኛ ህመም እየተሰማዉ ነዉ።
ሰዉነቱ በትኩሳት ግሎ ነገር ግን ብርድብርድ እያለዉ እየተንቀጠቀጠ ለሊቱን እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ
የመከራ ለሊት ይረዝማል ከታሰረ ሳምንት ወራት የቆየ ይመስለዋል ጠዋት ለህክምና የእስር ቤቱ ግቢ ካለዉ ክሊኒክ ለመሄድ ቢሞክርም ወረፋ ስላለ እንዲታገስ
ስለተነገረዉ መራመድ እያቃተዉ በልቡ
"መሞቴ ነዉ"
እያለ እንደምንም ፍራሹ ላይ ወድቆ ለመተኛት ሞከረ።

ቤዛዊት አይምሮዋ እየተረጋጋ ሲመጣ እማማ ስንቅነሽን ለፍፁም ምግብ እንዲቋጥሩለት አርጋ በተዘበራረቀ ስሜት ዉስጥ ሆና እንባ እየተናነቃት ወደ ፍፁም አመራች
እስካሁን ፍፁም ፍቃዱን መግደሉን አላመነችም
"የማይሆን የማይታሰብ ነገር"
ትላለች ከአፏ እያመለጣት ስትራመድ
የእስር ቤቱ ግቢ መግቢያ ስትደርስ የልብ ምቷ መፍጠን ጀመረ
ፍፁምን ካየችዉ ቆይታለች በፖሊሶች ታጅቦ ሲያልፍ ካየችዉ ወድያ ምንም የምታስታዉሰዉ ነገር አልነበረም እድሜ ለእማማ ስንቅነሽ እና ለልጃቸዉ ለጌታቸዉ ስታስቸግር ስትረብሽ ተንከባክበዉ ለዛሬ እንድትበቃ ላገዟት
ዉስጥ ገብታ የምትፈልገዉን ሰዉ ስም ተናግራ ቆማ መጠበቅ ጀመረች።
ፍፁም አይኖቹ ቀልተዉ ደም መስለዋል በተኛበት ፍራሽ እንደሰመመን "ፍፁም ደምሴ"
እየተባለ ሲጠራ ይሰማዋል መነሳት ግን አልቻለም
በሞት እና በህይወት መሀል ያለ እየመሰለዉ ሲያጣጥር ቆይቶ የቤዛዊት ምስል ፊቱ ላይ ድቅን ስላለበት አይኖቹ እንባ አዝለዉ እንደምንም ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ
"ፍፁም ደምሴ ጠያቂ መጥቶሎታል"
የሚል ድምፅ ስለሰማ እያቃሰተ ወደ ዘመድ ጥየቃዉ ቦታዉ ለመሄድ መታገል ጀመረ።
ቤዛዊት እንደሆነች አስቀድሞ ልቡ አዉቆታል ጥቂት እንደተራመደ ግን የማጥወልወል ስሜት
ስለተሰማዉ ለመረጋጋት አስቦ ለመቆም ሲሞክር ወደቀ ጨለማ እየታየዉ የነበረ ቢሆንም ቀስበቀስ ጨለማዉም ጠፍቶ እራሱን ስቶ ወድቆ ቀረ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍3
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ምእራፍ_ሁለት (#ክፍል_ሁለት)


#በክፍለማርያም

...ወድቆ ቀረ
ቤዛዊት ከዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ቆማ የፍፁምን መምጣት እየተጠባበቀች እንደ መለያ ከታጠረዉ ጥልፍልፍ የሽቦ አጥር መሀል ጥዉልግ ያለዉ ፍፁም እየተንቀራፈፈ ሲራመድ
እሱን እያየች ዉስጧ ስለተረበሸ በቆመችበት

"እኔን እኔን እኔን"

እያለች ለእሱ ያመጣችለትን ምግብ የያዘ ጎድጓዳ የምሳ እቃ መሬት ላይ እያስቀመጠች
በሁለቱም እጆቿ ደረቷን ለኮፍ ለኮፍ እያረገች መድቃት ጀመረች
"ምነው ለኔ ለበሽተኛዋ ባረገዉ እሱን ፈተዉ እኔን ባሰሩኝ"
ስትል ቆይታ ፍፁም መራመድ አቅቶት ሲቆም የእሷም ልብ በድንጋጤ ቆመ
መሬት ላይ ዝልፍልፍ እያለ ሲወድቅ እስዋም እንደሱ ወደ መሬት ተንበረከከች የለበሰችዉ ጥቁርበጥቁር ቀሚስ አዋራ ለበሰ ከአይኗ እንባ እንደ ዉሀ ትኩስ ሆኖ ጉንጮቿን አቁዋርጦ ይፈሳል
አጠገቧ የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች እና የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ሊያነሷት ቢጠጉም በጉልበቷ እንደተንበረከከች አንገቷን መሬቱ ላይ ደፍታ
"አስተማሪዬን አስተማሪዬን መልሱልኝ እኔ የሚያመኝን እሰሩኝና ፍፁሜን ፍቱልኝ"
ጩሀቷን የታመቀ ብሶቷን ማሰማት ጀመረች።

ፍፁምን እስረኞች በጥንቃቄ ደግፈዉ አቅፈዉ ወደ ክሊኒኩ ለመዉሰድ ሲሞክሩ ጠዋት የመለሰዉ ህክምና ወረፋ የሚያሲዘዉ ሰዉ እየተፀፀተ እና
"ምን አለ ጠዋቱኑ እንዲታከም በፈቀድኩለት"
በሚል ስሜት ዉስጥ ሆኖ ፍፁም ህክምናውን በፍጥነት እንዲያገኝ እረዳዉ
ፍፁም አይኑን ሲገልጥ ያስተዋለዉ አሁንም እስር ቤት ግቢ ዉስጥ መሆኑን ነዉ
አካባቢዉን እየቃኘ አንድ ወጣት ነጭ ገዋን የለበሰ ሀኪም መጥቶ
"ተከተለኝ"
አለዉ ፍፁምም ከተኛበት የክሊኒኩ አልጋ ቀስ እያለ ተነስቶ ተከተለዉ
ብዛት ያላቸዉ መድሀኒት ሰጥቶት ሰዐቱን ጠብቆ እንዲዉጥ ከመከረዉ በኋላ የደንብ ልብስ የለበሰ የማረምያ ቤቱ ፖሊት ወደ መታሰርያዉ ግቢ እየመለሰዉ።

መንገድ ላይ ለዘመድ ጥየቃ እንደተጠራ ሲያስታዉስ ከጎኑ ያለዉን ፖሊስ
"ዘመድ ፈልጎኝ ነበር እባክህ አንዴ ላናግራት"
አለ በተያያዘ አንደበት በህመም ቅላፄ ባለዉ አወራር
"ምንህ ናት"
ሲል ፖሊሱ ጥያቄዉን በጥያቄ መለሰለት
"ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ "
እየተንተባተበ መለሰለት
"ትንሽ አስቸግራ ነበር አልወጣም ብላ ትንሽ ቆይተን ተሽሎታል ሌላ ግዜ ነይ ስንላት ተመልሳ ሄዳለች"
አለዉና ፍፁም የታሰረበት ግቢ ሲደርሱ ለሌላኛዉ ፖሊስ አስረክቦ
"ፈጣሪ ይማርህ"
ብሎ ተለየዉ።

(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት በርቀት ፍፁምን በሽቦዉ አጮልቃ አፋፍሰዉ ሲወስዱት እየች
ሽቦዉን እየነቀነቀች መጮኋን አላቋረጠችም ነበር ፖሊሶች ሊያረጋጓት ቢሞክሩም የምትሰማበት ጆሮም ልብም አልነበራትም እናት አባት እንደተሞተበት ትኩስ ሀዘን ከልቧ አምርራ
"አረ ወገን አረ ፖሊስ አረ ወንድም አረ እህቴ"
እያለች ፊት ለፊቷ ያየችዉን ሰዉ ሁላ በለቅሶ እየለመነች
"አስፈቱልኝ አስለቅቁልኝ አስተማሪዬ እኮ ነዉ
ወደቀ እኮ ወ ደ ቀ አረ ላንሳዉ ኡኡኡኡ አረ የሰዉ ያለ..."
ልብሷ እንዳለ በአቧራ ተላዉሶ ፀጉሯን እያመነቃቀረች ደረቷን እየደቃች ስታስቸግር በሁኔታዋ ግራ የተጋቡት ፖሊሶች በስንት ልፋትና ትግል አረጋግተዋት ፍፁም ደህና እንደሆነና ህክምና እያገኘ እንደሆነ አስረድተዋት በፈለገችዉ ሌላ ቀን መጥታ ማየት እንደምትችል ነግረዋት እስከግቢዉ በር ደግፈው ሸኙዋት።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ምእራፍ_ሁለት (ክፍል ሶስት)


#በክፍለማርያም

ቤዛዊት ቤትዋን እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት ካረገች ሰነባበተች ይሄ ሁሉ ምስቅልቅል ይፈጠራል ብላ አልነበረም ወደ እነ እማማ ቤት አመጣጧ ፍፁምንም የጋበዘችዉ በነፋሻዉ አየር ከሰዉ እራቅ ብለዉ የሰላም የፍቅር ጊዜ ለማሳለፍ ነበር
ነገር ግን አንዳንዴ ሀሳብ እንደ ንፋስ የማይታይ ሆኖ ይነፍከሳል ሀይል ካለዉም ነገሮችን ሳይጠበቅ እያንሳፈፈ እንደሚወስደዉ የታሰበዉ ሳይሆን ቀርቶ ያልተጠበቀ ነገር ይፈጠራል
ከእስር ቤቱ በር ጥቂት እንደወጣች ድንጋይ አጊንታ አረፍ አለች ጭንቅላቷ ዉስጥ ፍፁም ሲወድቅ ያለዉ ሁኔታ አሁንም ይታያታል አይኖቿ በለቅሶ ብዛት እንባ ማዉጣት ቢያቅታቸዉም ለአመል በቀስታ የሚፈሱ የእንባ ዘለላወች የአፍንጫዋን መስመር አቋርጠዉ አፍዋን እያራሱ በአገጯ አርገዉ ልብሷን እያረጠቡት ነዉ።

"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
በልቧ ይሄን ቃል ታነበንባለች እስካሁን መታሰሩ እዉነት አልመስልሽ እያላት እራሷን
"እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ"
እያለች ትጠይቃለች መመለስ እና መፍታት የማትችለዉ ጥያቄ ሲሆን አይምሮዋ እየተቃወሰም ቢሆን ከተቀመጠችበት ተነስታ እንባዋን በእጆቿ እያበሰች ወደ እነ እማማ ስንቅነሽ ቤት አመራች።

ፍፁም ለመጀመሪያ ግዜ መድሀኒቱን ዉጦ የሰላም እንቅልፍ ወሰደዉ በህልሙ
ቤዛዊት ፊት ለፊቱ ተቀምጣ ስትስቅ እያያት ከጀርባዋ ጥቁር አሞራ እየበረረ ትከሻዋ ላይ ተቀምጦ የማያስፈራ ድምፅ እያወጣ ሲጮህ ባኖ ተነሳ
እየነጋጋ ነበር ከእስር ቤቱ ሚዲያ ክፍል መዝሙር ድምፁ ከፍተደርጎ ተከፍቷ ይሰማዋል እስረኞች ከእንቅልፋቸዉ እየተነሱ ወደ ዉጪ እየወጡ ነዉ ተነስቶ ለመቀመጥ ሞከረ ህመም አልተሰማዉም ተነስቶ ቆመ እራሱን ለቆታል
ፊቱ ላይ ጥልቅ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታይቶ እየተራመደ ወደ ዉጪ ወጣ አለ።
ቤዛዊት ከተኛችበት ስትነቃ የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ በጥቂት ተገልጧ ወደ ሚታየዉ ባቷ ሲያፈጥ ያዘችዉ ቀሚሷን እያስተካከለች ተነሳች ጌታቸዉ ግን አሁንም በአይኑ እየተከታተላት ነዉ
"ቆንጆ እንደሆንሽ ታዉቂያለሽ"
አላት ማታ የጠጣዉ መጠጥ አሁንም አለቀቀዉም አፉን አሳስሮታል
ቤዛዊት ልብ ብላ አልሰማችዉም እማማ ስንቅነሽ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በጠዋት ስለወጡ ሁለቱ ብቻ ናቸው ቤቱ ዉስጥ ያሉት።

(ከደቂቃ በፊት)
ቤዛዊት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ዉስጥ ሆና እማማ ስንቅነሽ
"ልጄ ቤዛዊት ቤተስኪያን ደርሰን እንምጣ"
እያሉ ሊቀሰቅሷት ቢሞክሩም አልሰማም ስላለቻቸዉ እሳቸዉ ደጅ ወጥተዉ ልብሳቸዉን ቀያይረዉ ነጠላ ቢጤ ደርበዉ እንደወጡ በሩን ለመዝጋት ሲሞክሩ ልጃቸዉ ጌታቸዉ ከእንቅልፉ ይነቃል
ጥቂት አልጋዉ ላይ ሆኖ ስለ ቤዛዊት ቆንጅና ስለ ገላዋ ስለ ሰዉነቷ በህሊናዉ ሲስል ቆይቶ በቀስታ ከአልጋዉ ይነሳና ወደ እማማ እና ቤዛዊት ወደ ተኙበት ክፍል ያመራል
ቤዛዊት ብርድ ልብስ ተሸፋፍና ጥቅልል ብላ ተኝታለች ጌታቸዉ ፊት ለፊቷ እያያት ከቆመ በኋላ ብርድ ልብሱን ቀስ አርጎ ገለጠዉ ቤዛዊት አሁንም የእንቅልፍ ልብ ዉስጥ ናት
ቀስ ብሎ እረጅሙን ቀሚሷን እየገለጠዉ እና ታፋዋን እየተመለከተ ቤዛዊት ተገላብጣ ስትነቃ ፈንጠር ብሎ ቆሞ ማየቱን ቀጠለ።

(አሁን)
ጌታቸዉ ከቤዛዊት ጀርባ ቀስ ብሎ እየተጠጋ ሊያቅፋት ሲሞክር
"ምን መሆንህ ነዉ"
እያለች ገፍትራዉ አይኗን አጉረጠረጠችበት
እንደ መፍራት እያለ
"ምንም ምን አረኩ ደህና መሆንሽን ለማወቅ ነው "
እያለ ወደኋላ አፈገፈገ ነገር ግን በልቡ መጥፎ ሀሳብ ጠንስሶ ጠብቂ አገኝሻለሁ እያለ ነበር።

"ደህና ነኝ "
እያለችዉ ቤዛዊት ዛሬስ ፍፁምን አየዉ ይሆን እያለች እራሶን እየጠየቀች ለእራሷ
ዛሬማ አገኘዋለሁ አዋራዋለሁ እያለች ወጣች።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ምእራፍ_ሁለት ( #ክፍል_አራት)


#በክፍለማርያም

..ፍፁም ወረቀቱን ገልጦ ስለቤዛዊት እና ስለሱ መከራ የበዛበት የፍቅር ታሪክ መፃፉን ተያይዞታል
ህመሙ እየተሻለዉ ስለሆነ ጥሩ ስሜት ዉስጥ ነዉ ስላለፈዉ ታሪክ እያሰበ ይፅፋል አስደሳች ጊዜወቹ ታዉሰዉት ፊቱ ላይ ደማቅ ፈገግታ እየተነበበ አእምሮዉ ላይ ያለዉን ከወረቀቱ ጋር እያዋሀደዉ ነዉ።

እንደምትወደዉ የነገረችዉን ቀን አስታወሰ ፅፋ የሰጠችዉ ወረቀት ዉል አለበት የተጣሉበትን ቀን መሀል ላይ ፍቃዱ መሀላቸዉ ገብቶ የእህቱን ፎቶ ሚስቱ ናት ብሎ ያወራ ቀን የተፈጠረዉን ሲያስታዉስ የሚፅፉት እጆቹ መንቀጥቀጥ ጀመሩ
ለቤዛዊት ሊያስረዳት ዉሸት መሆኑን ሊያብራራላት ሲጣደፍ መኪና የገጨዉን ሲያስታዉስ መፃፍ ስላልቻለ እስኪቢርቶዉን ወረቀቱላይ ጥሎ በዝምታ ተቀመጠ
ከጎኑ አብሮት የታሰረዉ ማስረሻ የተባለ ታሪሚ የፍፁምን ሁኔታ በአይኖቹ ሲከታተል ስለነበረ
"ምን እየፃፍክ ነዉ ወዳጄ?"
ሲል ለዉቀት መከላከያ ብሎ ዉሀ ዉስጥ ነክሮ አናቱ ላይ ያስቀመጠዉን ፎጣ እያወረደ
ፍፁም የጠየቀዉን ልጅ ትኩር ብሎ ተመለከተዉ ማስረሻ ቀጠን ብሎ ቀዉላላ የሚባል ወጣት ነዉ አይኖቹን ሲያስተዉላቸዉ ከተረገመዉ ፍቃዱ ጋር ተመሳሰሉበት
ለመጀመርያ ግዜ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጮሀ
"ምን አገባት ምን አገባህ"
ደም ስሮቹ ተገታትረዉ ንዴት እያንቀጠቀጠዉ መናገሩን ተያያዘዉ
"ለምን አተወኝም ተዉኝ ተዉኝ"
እጆቹን እያወራጨ ወደ ማስረሻ ተጠጋዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየተገረመ እና ጥሎት እንደመሄድ እያለ
"እብድ ድሮስ ነብሰ በላ መጨረሻዉ ማበድ ነዉ"
ብሎት ወደ ዉጪ ፍፁምን ትቶት ወጣ።
ፍፁም ግን ማስረሻ የተናገረዉ ንግግር አይምሮዉ ላይ እያቃጨለበት ነበር
"ነብሰበላ ነብሰ በላ ማበድ ማበድ"
እዉነት ነዉ የሰዉ ደም ወደ ሰማይ ይጮሀል ገዳይም የሰላም እንቅልፍ አያገኝም ማንም መጥፎ ሰው ቢሆን እንኳን የፈጠረዉ ፈጣሪ በሞት ካልወሰደዉ በቀር በሰዉ ቢገደል
ገዳዩ ሀጥያቱን ይሸከማል
ቤዛዊት መንገድ ላይ ወደ እስር ቤቱ አቅራቢያ ስትደርስ ካገኘችዉ ጥሩ ምግብ ይሰራሉ ብላ ካሰበችበት ምግብ ቤት ገብታ ለፍፁም በገዛችዉ ሰፊ የምግብ መያዣ ምግብ አስቋጠረችለት
ደስ እያላት ነው በልቧ ፍፁምን ዛሬ እንደምታገኘዉ እንደምታዋራዉ እርግጠኛ ሆናለች።
ዘመድ መጠየቅያዉ ቦታ ላይ ቆማ የፍፁምን ሙሉ ስም ተናግራ መጠበቅ ጀመረች
ፍፁም ከላይ የተጣበቀ ቲሸርት ከስር ያረጀ ቁምጣ በሲሊፐር ለብሶ ሲመጣ በርቀት ተመለከተችዉ ልቧ እየተረበሸ ነዉ አሳዘናት የሴትነት አንጀቷ ባሀሪዋም እሩሩ ስለሆነች ሆድ ብሷት እንባ ማንባት ጀምራ ሲያየኝ እሱም ይጨነቃል ብላ አስባ እንባዋን ወድያዉ ጠራረገች።
የያዘችዉን ምግብ ፖሊሶቹ ፊት ለፊታቸዉ እንድትጎርስ አዘዟት እየጎረሰች ፍፁምን በከርታታ አይኗ እያየችዉ ነዉ ፍፁም አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬቱን እያየ ምግቡን በግዴለሽነት ተቀብሏት
መሬት ላይ አስቀምጦ በጨረፍታ እያያት
"ለምን ተቸገርሽ ለኔ ብለሽ መልፋት የለብሽም እኔ የብዙ አመት ፍርደኛ ነኝ..."
የጀመረላትን ሳታስጨርሰዉ
"ሁሌም ቢሆን እጠብቅካለሁ ሁሌም"
ቅድም ያስቆመቻቸዉ እንባወቿ መፍሰስ ጀመሩ።
"አስራ ምናምን አመት..."
አለና የፌዝ ሳቅ ሳቀ
ፍፁም እራሱ ማስረሻ ካዋራዉ ጀምሮ ፀባዩ እየተቀያየረ ነበር ዉስጡ ሰላም እየተሰማዉ አደለም
እሱ በእስር እየበሰበሰ የወጣቷን የቤዛዊትን ህይወትም የቁም እስር ዉስጥ አትክተተዉ የሚል እርኩስ መንፈስ ልቡ ዉስጥ ማደግ እየጀመረ ነበር መንፈሱ ህፃን ስለሆነም እያነጫነጨዉ ነዉ።
"እንዋደድ የለ አትወደኝም ስትል ጠየቀችው ?"
ቤዛዊት አይን አይኑን እያየች
"እወድሻለሁ"
አላትና ጥቂት አስቦ
"ነብሰ ገዳይ ሰው ግን ላንቺ አይጠቅምሽም ሌላ አዲስ ህይወት መጀመር ትችያለሽ አልቀየምሽም ባንቺ ደስተኛ ነኝ ሁለተኛ ግን እኔ ጋር እንዳትመጪ"
አላትና አይኗን ላለማየት እየተጣደፈ ሳይሰናበታት ወደ እስር ቤቱ አመራ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አምስት


#በክፍለማርያም

....ወደ እስር ቤቱ አመራ
ከጀርባው በህይወቴ አጊንቼ አጣሁዋት ብሎ በትዝታ በናፍቆት እስሩን እስኪጨርስ ከልቡ የማያወጣትን ቤዛዊትን ጨክኖባት ትቷት ጀርባውን ሰጥቷት ከእይታዋ እየራቀ ሄደ
እየተራመደ ዞረህ ተመለስ ዞረህ አዋራት ተስፋ ስጣት ስወጣ ተጋብተን ልጆች ወልደን በፍቅር እንኖራለን በላይ የሚለዉ ስሜት ቢኖርም
መጥፎዉ ስሜት በተቃራኒዉ የምን ተስፋ ነዉ የምታስበዉ ልጅቷም ህይወት አላት አንተ ህይወትህ አበቃ ታሰርክ እና እስዋ ሌላ ህይወት የላትም የሚለዉ ስሜት አሸንፎ ወደ ኋላም ሳይዞር እየተንቀራፈፈ እየተጎተተ መራመዱን ቀጠለ።

ህይወት ግን እስትንፋስ ይዛ እስከቀጠለች ድረስ የሚፈጠረው አይታወቅም አበቃ ተዘጋ ተደመደመ የተባለዉ አንድ ቀን ጊዜዉን ጠብቆ ይጀምራል ይከፈታል
ተጀመረ ተከፈተ የተባለዉም በድንገት ሊዘጋ ይችላል
ህይወትንም ዉስብስብ የሚያረጋት ገፅታ ይሄ ነዉ የተዘጋዉ በር ሲከፈት የሚገኘዉ ደስታ እና የተከፈተዉ በር ሲዘጋ የሚገኘዉ ሀዘን ሲፈራረቅ የህይወት መስመርም ከዚህ ጋር ተቆራኝቶ ይሄዳል።

ቤዛዊት ከአይኗ እየራቀ ያለዉን ከቤተሰብ ከአባት ከእናት ከእህቷ ያስበለጠችዉ ፍቅርን በእሱ የጀመረችዉ ሰዉ እርቋት ሲሄድ በቆመችበት ምንም ሳትንቀሳቀስ ከአይኗ እስኪርቅ ካየችዉ በኋላ በጥልቅ ዝምታ ዉስጥ ሆና መራመድ ጀመረች።

ትላንት ስትጮህ ስታለቅስ ያዩዋት የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች
"እንዴት ነሽ እህት..."
እያሉ ሊያዋሯት ሊያፅናኗት ቢሞከሩም ልትመልስላቸዉ ልታዋራቸዉ ይቅርና በዙርያዋ ምን እንደሚፈጠር ሁሉ የምታዉቅ አትመስልም
የቀኝ እጇን የሌባ ጣት ጥፍር አፍዋ ዉስጥ ከታ እየቆረጠች ቢመስላትም በሀሳብ ግን ጀርባዉን ሰጥቷት የሄደዉን ፍፁምን እያሰበች
ህመሞም መጣሁ መጣሁ እያለ አይኖቿ ፍዝዝ እያሉ ትራንስፖርት ይዛ ከኋላ ወንበር ተቀምጣ መጉዋዝ ጀመረች።

"እናቱ ሂሳብ"

በተደጋጋሚ ይጮሀል የታክሲዉ ረዳት ቤዛዊት የፈዘዙት አይኖቿ እየቀሉ ታክሲዉ ላይ ከተለጠፈዉ ጥቅስ ላይ አይኖቿን ተክላ እየሰማችዉ አደለም
ከጎኗ የተቀመጠችዉ ተሳፋሪ ቤዛዊት የምታየውን ጥቅስ አየችዉ
"ቀን ሲጥል ፈራጁ ብዙ ነዉ"
የቤዛዊትን አይኖች ስታይ የሆነ ችግር ዉስጥ ያለች ስለመሰለቻት
"ከኔ ላይ ቁረጥ"
ብላ ለእረዳቱ እየነገረችዉ ወደ ቤዛዊት ተመልሳ ዞራ
"ደህና ነሽ ?"
ስትል ጠየቀቻት የቤዛዊትን ትከሻ ነካ ነካ እያረገች
ቤዛዊት አጠገቧ እያዋራቻት ያለችዉን ልጅ በሚንከራተቱት አይኖቿ እያየቻት
"እ ኔ እንጃ "
ስትል መለሰችላት
"እና አሁን ወዴት እየሄድሽ ነዉ?"
ለቤዛዊት አዝናላት አሟት ይሆን ስትል እያሰበች ልትረዳት ፈልጋ
አለም ላይ ብዙ የሰዉን መጥፎ ማየት የሚፈልጉ ለሰው መልካም የማያስቡ የተረገሙ ሰወች ቢኖሩም ሌሎች ለቁጥር የሚታክቱም ደግ እና መልካም ሰወችም አሉ።
"እማማ ስንቅነሽ ቤት እየሄድኩ ነዉ"
ቤዛዊት አፏ እየተሳሰረ ነገረቻት
ተሳፉሪዋ ከቤዛዊት ጋር አብራት ወርዳ የምትሄድበትን ቀጠሮ ሰርዛ ለመራመድ አቅም ያጣችዉን
ለህመሞ መነሳት ቋፍ ላይ ያለችውን ቤዛዊትን እያታለለች በዘዴ የእማማ ስንቅነሽን ቤት አቅጣጫ እያወጣጣቻት በእግር መጉዋዝ ጀመሩ።

"እማማ ስንቅነሽ እርሶ ኖት አደል"
አለች ተሳፋሪዋ የእማማን ግቢ ቆርቆሮ አጥር አልፈዉ ሲገቡ ቤዛዊትን ገብታ እንድትተኛ እየነገረቻት በእድሜ ገፋ ያሉ ሴትዮ ስታይ እማማ ስንቅነሽ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ ብላ
እማማ ለልጅቷ መልስ አልመለሱላትም ፈዛ ነዉልላ የቆመችዉን ቤዛዊትን እሮጠዉ አጠገቧ ደርሰዉ በእጃቸዉ ፊቷን እየደባበሱ
"ምን ሆንሽብኝ ምትኬ ምን ነካብኝ "
እያሉ ደግፈዋት ወደ ዉስጥ ካስገቧት በኋላ አልጋ ላይ እንድትተኛ ነግረዋት ልጅቷን
"የተባረክሽ ልጅ ፈጣሪ ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሽ ግቢና ሻይ ጠጪ"
እያሉ እየመረቁ እንድትገባ ቢለምኗትም
"ሌላ ግዜ እመጣለሁ"
እያለች
"ልጆትን ፈጣሪ ይማርሎት"
ብላ ተሰናብታ ወጣች።
ቤዛዊት የአልጋዉን ፍራሽ እየነጨች መሬት ላይ እንደ ቄጤማ እየጎዘጎዘችዉ ነበረ።

💫ይቀጥላል...💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_ስድስት


#በክፍለማርያም

...እየጎዘጎዘች ነበር
እማማ ስንቅነሽ እንግዳዋን ሸኝተዉ የቤዛዊት ጤንነት ፊቷን አንብበዉ እየሰጉ
"ደሞ እንዳይጀምራት"
በልባቸዉ እያሉ ወደ ቤታቸዉ ወደ ዉስጥ ሲዘልቁ ቤታቸዉ በብጥስጣሽ እስፖንጅ ተሞልቶ ቤዛዊት የማይሰሙ ቃላቶች እያነበነበች በእጆቿ ቀሪዉን የፍራሹን አካል እየቧጠጠች እና እየነጨች እየወረወረችዉ ነበር።

እንባ ተናነቃቸዉ በድህነታቸዉ በቅጡ የማያዉቋት ሴት በልፋት የገዙት ፍራሽ ተበታትኖ በማለቁም አልተፀፀቱም ሁሌ የቤዛዊትን ሲያዩዋት በህይወት የሌለችዉን ልጃቸዉ ስለምትታያቸዉ እንደ ልጃቸዉ ህመም አስበዉ
"ቤዛዊቴ ቤዛዊት ምን ሆንሽብኝ ምን ነካብኝሳ"
ከጎኗ እንደ ህፃን ልጅ ኩርምት ብለዉ ተቀመጡ
ቤዛዊት መልስ አልመለሰችላቸዉም እጆቿ ይቧጥጣሉ ከባድ ስራ እንደያዘ ሰዉ ተመስጣ ጥፋት ታጠፋለች ለእሷ የሚታወቃት ነገር የለም
"እ እህህ እህህህ እህ እህ እህህ"
ነገር እንደሚበላ ሰዉ ከንፈሮቿን በቀስታ እያኘከች ታጉተመትማለች የምታስበዉ ለእማማ ስንቅነሽ ስላልገባቸዉ እያቀፏት እና ፍፁም ብላ ያወራችላቸዉ ሰዉዬ ትዝ ብሏቸዉ
"ፍፁም ጋር ሄደሽ ነበር?"
ሲሉ ጠየቋት
ቤዛዊት የፍፁምን ስም እንደሰማች እማማ ስንቅነሽ ላይ አፈጠጠችባቸዉ
"ፍፁም ፍፁም ፍፁም"
ቃላቶቹን እየደጋገመች አይኖቿን እማማ ስንቅነሽ ላይ ተክላ ቆይታ
"ቤቴ ልሂድ ፍፁም አይመጣም"
አለችና ትንሽ እንደማሰብ ብላ
"ይመጣል እንዴ?"
እማማ ስንቅነሽን አፋጠጠቻቸዉ
"ታስሮ የለ ሲፈታ ይመጣል"
አሏት የእርጅና ነገር ሀቅ ሀቁን ሳይደብቁ እያወሩ
ቤዛዊት የሆነ ነገር ያሰበች ይመስል የእማማ ስንቅነሽን የተገነጣጠለ ኮርኒስ ላይ ካፈጠጠች በኋላ
"አይጥ ማታ ማታ በዚህ ላይ ይሄዳል አደል
እኔኮ አይጥ እፈራለሁ..."
እማማ ስንቅነሽ እንዳመማት በጤናዋ እንዳልሆነች አሁን አረጋገጡ እንባ ያቀረረ ፊታቸዉን በነጠላቸዉ እያበሱ የቆመችዉን ቤዛዊትን ወደ እራሳቸዉ አልጋ ወስደዉ እያስተኟት
"አይ ሰዉ መሆን"
እያሉ እየተብከነከኑ ቤዛዊት እንቅልፍ እስኪወስዳት ፀጉሯን እየደባበሱ አስተኝተዋት ሰካራሙ ልጃቸዉ ጌታቸዉ እንዲገባ በሩን ሳይቀረቅሩት ዘጋ አርገዉት ከጎኗ እሳቸዉም ስለቤዛዊት እና ስለበፊት ልጃቸዉ መመሳሰል እያሰቡ አሸለቡ።

ፍፁም ቤዛዊትን አዋርቶ እንደተመለሰ እሱ የሚተኛበት አቅራቢያ አናቱ ላይ ፎጣ የደረበ ሰዉ ወረቀት እያነበበ አይቶ እንዳላየ ሊያልፈዉ ሲል ማስረሻ መሆኑን ሲያረጋግጥ ፍቃዱን እንዳያስታዉስበት ፊቱን አዙሮ አልፎት ቦታዉ ደርሶ እንደተቀመጠ የቤዛዊትን እና የሱን ታሪክ የፃፈበት ወረቀት ከቦታዉ እንደሌለ ሲያስታዉስ እንደማበድ አረገዉ።
ፍቃዱን በያዘዉ ክራንች በንዴት አናት አናቱን ሲመታዉ የነበረዉ ሁኔታ አይምሮዉ ላይ ታየዉ
ክራንቹ በፍቃዱ ደም ተላዉሶ የፍቃዱ ፀጉር በደም ተለዉሶ ታየዉ አፉ ዉስጥ የሚጎመዝዝ ነገር ያለ እየመሰለዉ ምራቁን እየተፋ እየተበሳጨ ወደ ማስረሻ ተንደረደረ
"አምጣ የወሰድከዉን አምጣ አምጣ"
ሲል ማስረሻ ላይ አንባረቀበት
ማስረሻ የፌዝ ሳቅ እየሳወቀ
"እብድ አፍቅረህ ነዉ ለካ"
ሲል በንቀት ወረቀቱን የፍፁም ፊት ላይ በተነለት
"ቤዛዊት እብድ አደለችም "
መሬት ላይ የተበተነዉን ወረቀት እየሰበሰበ አጣጥፎ ኪሱ ዉስጥ ከከተተ በኋላ
"ቤዛዊትን እብድ እንድትላት ማን ፈቀደልህ
ማንስ ህይወቴን አንብብ አለህ"
ፍፁም በንዴት እየተለዋወጠ ነዉ
ማስረሻ በፍፁም ሁኔታ እየሳቀ ነዉ
በቀልድ ለዛ ባለዉ ንግግር
"ታሪክህ ሰዉ በመግደል ስላለቀ ያሳዝናል"
አለዉና አክሎበት
"ቤዛዊትን አንዱ ላፍ ያረግልሀል ኪኪ ኪኪኪ ኪኪኪኪኪ"
ተንከተከተ
አብዛኛው ሰዉ በታሪክህ ይስቅብሀል በዉድቀትህ ያላግጥብሀል በድክመትህ ይመጣብሀል
ቀን ሲጥልህ ብዙ ብዙ ነገሮች ይቀያየሩብሀል ከተከበረ አስተማሪነት ወደ ወንጀለኛ በአንዴዉ ስትለወጥ የሰዉ ደም አእምሮህ ዉስጥ ሲመላለስ ፍቅር ያልከዉ ነገር እሩቅ ሲሆንብህ አለም የተደፋችብህ ሲመስልህ የምታየዉ የሚያጋጥምህ ነገር ሁሉ አስከፊ ይሆናል
"ምንድነዉ ያልከዉ"
አለ ፍፁም ሁለቱንም እጆቹን ገትሮ ፊቱ ተቀያይሮ ወደ ማስረሻ አንገት እየተንደረደረ ደርሶ ማስረሻን ሲጥ አርጎ ይዞት ተያይዘዉ ወደ መሬት ወደቁ ማስረሻ ከስር ተኝቶ ይንፈራፈራል ፍፁም
ከላይ ያለ የሌለ ሀይሉን ተጠቅሞ አንቆታል።

💫ይቀጥላል ...💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_ሰባት


#በክፍለማርያም

በቅርብ እርቀት የነበሩ እስረኞች ለማገላገል መሯሯጥ መጯጯህ ጀመሩ
የተጣሉትን ሁለቱንም ሰወች በመከራ አለያዩዋቸዉ በፍጥነት ባይደርሱ ከባድ ነገር ይፈጠር ነበር
ፍፁም ኑሮ አለሙ ህይወቱ የጠፋ ስለመሰለዉ ተስፋ ቆርጧል
"ከዚህ በላይ ምን መከራ ይፈጠራል ከእስር ሳልፈታም እዚሁ ልሞት እችል ይሆናል ታስሬ ተቀጥቼ እንኳን እንደ ፍቃዱ አይነት መሰሪ ሰዉች ለምን አይተዉኝም"
ሲል በልቡ ይጠይቃል
የእስረኞችን መጣላት እና የገላጋዮችን መጯጯህ የሰሙ የማረምያ ቤቱ ፖሊሶች ዱላቸዉን ይዘዉ እየሮጡ ገቡ ፍፁም ማስረሻን ለቆት ጭንቅላቱን ይዞ ቆሟል ማስረሻ አንገቱን እየነካካ
"ይሄ ሰዉዬ ጤነኛ አይመስለኝም "
እያለ ያወራል
ከፖሊሶቹ አንዱ
"የተጣላችሀት ሁለታችሁም ተከተሉኝ "
ሲል ትህዛዝ ሰጠ ፍቃዱና ማስረሻ በሌላ ፖሊስ ተይዘዉ ወጡ
አንድ ረዘም ያለ ዱላ የያዘ ፖሊስ ዉጪ የነበሩት ሌሎች እስረኞች ወደ ቤታቸዉ ዉስጥ እንዲገቡ ሲያዝ ሁሉም ወደ የክፍሉ ገብቷ ግቢዉ ጭር አለ
ጭር ካለዉ ግቢ ዉስጥ ጥቂት ፖሊሶች እና የተደባደቡት ሁለቱ እስረኞች እየተፋጠጡ ለጥቂት ግዜ በመሀላቸዉ ዝምታ ሰፍኖ ቆይቶ
ፍፁምን እና ማስረሻን እያፈራረቀ ፖሊሱ እያያቸዉ
"የምን ጥጋብ ነዉ የሚያጣላችሁ"
ሲል ሁለቱም ላይ ጮሀባቸዉ ከእግር እስከራሳቸዉ በአይኑ እየቃኛቸዉ
ማስረሻ ፈጠን ብሎ
"እሱ ነዉ እኔ አደለሁም...."
እያወራ ፖሊሱ በያዘዉ ዱላ የማስረሻን እግር እየቀለጠመዉ
"ወረኛ አትለፍልፍ ዳይ ቁጭ ብድግ"
አለና ለመማታት ዱላዉን ሲያነሳ ማስረሻና ፍፁም ቁጭ ብድግ ማለቱን ተያያዙት
"እዚህ የመጣችሁት ፀባያችሁን እንድታርሙ መሰለኝ"
ፖሊሱ ቆጣ ብሎ
ፍፁም እግሩም ችግር ስላለበት እያመመው እየደከመዉ ከማስረሻ እኩል ተቀምጦ መነሳት ሲያቅተዉ ለመጀመርያ ግዜ ዱላ አረፈበት ሀይለኛ ህመም ተሰማዉ ጀርባዉን በድጋሜ በዱላዉ ሲደግመዉ በእልህ ከማስረሻ እኩል መስራት ጀመረ።
"ዳይ እንደዛዉ ቁጭ ብድግ እያላችሁ እዛ ጋር ደርሳችሁ ኑ"
ፖሊሱ ሌላ ትህዛዝ አዘዘ ወደ ኋላ የቀረ ዱላ እየቀመሰ ነበር።
ፍፁም ግን መሀል ላይ እግሩ መንቀሳቀስ ስላልቻለ መሬቱ ላይ ላቡን እየጠረገ ተቀመጠ ማስረሻም እያለከለከ ነበር
ፖሊሱም እየገላመጣቸዉ
"ሁለተኛ ፀብ ዉስጥ እንዳላገኛችሁ"
ብሎ ዝቶባቸዉ ትቷቸው ሄደ።

የእማማ ስንቅነሽ ልጅ ጌታቸዉ ለሊት እንደገባ መብራት አብርቶ ቤዛዊትን በአይኑ ፈለጋት ከእናቱ አጠገብ ሽጉጥ ብላ ተኝታለች
"ጠዋት አገኝሻለሁ"
ሲል በተኮለታተፈ ድምፅ አወራ
የቤዛዊትን ገላ መመኘት ከጀመረ ሰነባብቷል በህልሙ ሳይቀር ትታየዋለች መጠጥ እየጠጣ የሚያስበው ቤዛዊትን በፍቅርም ይሁን በጉልበት ገላዋን አቅፎ ለመቅመስ ሲቋምጥ ነበር
በፍቅር እንደማይሆን ከንግግሯ ከሁኔታዋ ስለተረዳ በጉልበት አሰገድዶ ሊደፍራት እማማ ስንቅነሽ የማይኖሩበትን ቀን በጉጉት እየጠበቀ ነዉ
ሁሌ በጠዋት ደሞ እናቱ ቤተክርስቲያን ስለሚሄዱ
"ነገ እቅዴን ለማሳካት ሁነኛ ቀኔ ነዉ"
እያለ ወደ ጉዋዳ መኝታዉ እየንገዳገደ ገባ።

ሲነጋጋ በጣም በጠዋት የተነሱት እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊትን ሰላም ማደር በእጃቸዉ ዳበስ ዳበስ አርገዉ ካረጋገጡ በኋላ ወደ ቤተክርስቲያን አመሩ።
ለክፋት እንቅልፍ አጥተዉ የሚያድሩ አይኖች አሉ ሰዉን ለማዋረድ ለመጣል ጉድጉዋድ የሚቆፍሩ እጆች አሉ
ምንም ቢሆን ግን በመጥፎ ጎንህ በማታዉቀዉ የኔ ብለህ በተጠጋሀዉ ወዳጄ ባልከዉ ሰዉ መጠቃት ደሞ ህመሙ እጥፍ ድርብ ነዉ
የእግራቸዉን መዉጣት ሲጠባበቅ የነበረው ጌታቸዉ ሹክክ እያለ ከተኛበት ተነስቶ በሩን ከቀረቀረዉ በኋላ ቤዛዊት የለበሰችዉን ብርድ ልብስ ጎትቶ መሬት ላይ ጣለዉ።

💫ይቀጥላል ..💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍21
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_ስምንት


#በክፍለማርያም

...ብርድ ልብሱን መሬት ላይ ጣለዉ
ጌታቸዉ የለበሰዉን ሱሪ እያወለቀ ከእንቅልፏ ያልነቃችዉን አይምሮዋ በትክክል እያሰበ ያልሆነዉ ምስኪኗ በሽተኛዋ ቤዛዊት ላይ ተከመረባት
የቤዛዊት አይኖች በድንጋጤ አብርተዉ መቁለጭለጭ ጀመረች የት እንዳለች ለማስታወስ አልቻለችም እላይዋ ላይ የተከመረ ነገር እንዳለ ለማዉረድ እየታገለች ነበር
አቅም ግን እያነሳት ሲመጣ ዝልፍልፍ ብላ ተሸንፋ የጌታቸዉ መጫወቻ ሆነች።

ቀሚሷን አዉልቆ የዉስጥ ሱሪዋን እያወለቀዉ መታገሏን ስላቆመች
"ምን አስባ ነዉ"
ብሎ ለአፍታ ተመለከታት
አንገቷ ወደ ቀኝ ዘመም ብሎ በትራስ ተደግፎ ከአፏ ምራቅ ይወርዳል አይኗቿ እንደቀሉ ናቸዉ ህመሟ ብሶባታል እሷ አደለችም ስትታይ አንጀት ትበላለች
እላይዋ ላይ የተከመረዉ ሰዉ ግን ስሜቱ አሸንፎት ህመሟ አይታየዉም ቢታየዉም ምንም አልመሰለዉም የእሱንም የዉስጥ ሱሪ ቀስ ብሎ አዉልቆት ተገናኛት እላይዋ ላይ መጨፈር ጀመረ
የቤዛዊት አይኖች ግን ካረጀዉ ኮርኒስ ዉስጥ የሚፈሩት አይጥ መኖር አለመኖሩን ፈዘዉ እያዩ ይመራመራሉ።

ፍፁም በጠዋት ቤዛዊት ያመጣችለትን ምግብ ሊበላ ሲከፍተዉ እስረኞች አብረዉት ሊበሉ ከበቡት
ከእነሱም መሀል ፎጣ አናቱ ላይ የማይለየዉ ማስረሻ ሁሉ ነገር አብቅቷል የትላንቱ ፀብ ተረስቷል ብሎ ለመጉረስ እጁን ዘረጋ ነገር ግን በዘረጋዉ እጁ እንጀራ ጠቅልሎ ወደ አፉ እያስጠጋ የፍፁም ቡጢ አርፎበት እጁ ላይ የነበረዉ ምግብ ተበታተነ ማስረሻ ግን ለመማታት እጁን አልዘረጋም የተቀጡት ቅጣት አስተምሮት ነበር
ፍፁም አንድ ቡጢ ሰንዝሮ አልበቃዉም ማስረሻ ሆድ ላይ ተቀመጠ
በተመሳሳይ ስዓት ቤዛዊት ገላ ላይ ጌታቸዉ ተቀምጧባት ነበር
ፍፁም እየደጋገመ ቦክስ መሰንዘር ማስረሻን ማድማት ጀመረ
በዛዉ ሰዐት የታመመችዋ ቤዛዊት ምስኪን ልብ እየደማ ነበር
ፍፁምን እስረኞች ተረባርበዉ ከማስረሻ ሰዉነት ላይ አነሱት ማስረሻ በደም ተላዉሶ እያቃሰተ ነዉ
ፖሊሶች እየተሯሯጡ መጡ በአሁኑ ለፍፁም አላዘኑለትም እያዳፉ እየገፈታተሩ ከግቢዉ ይዘዉት ወጥተዉ ለብቻ ሰዉ የሚታሰርበት ጨለማ እና አስፈሪ ጠባብ ክፍል ዉስጥ ወርዉረዉ ቆለፉበት
ፍፁም እራስህን አጥፋ አጥፋ የሚል ጥሪ ጭንቅላቱ ዉስጥ ሲያቃጭልበት እራሱን እንዴት ማጥፋት እንዳለበት እያሰበ
"መሞት አለብኝ"
ሲል ደመደመ በሀሳብ ዉስጥ ሆኖ እጆቹን ወደ ኪሱ ሲከት የእሱን እና የቤዛዊትን ከመጀመርያው ጀምሮ የያዘዉን ወረቀት ነካዉ አዉጥቶ በደበዘዘ ብርሀን ለማንበብ ሞከረ
ወደ ቤቴ እያነከስኩ ስገባ አልገዬ ላይ ተኝታ ጠበቀችኝ ሳያት ደስ አለኝ አጠገቧ እንዳልቀሰቅሳት ተጠንቅቄ ተኛሁ ነገር ግን ነቅታ በአይኖቿ እያየችኝ የዛን ለት ክብሯን ሴትነቷንም ሰጠችኝ.....
ይሄንን አያነበበ የመሞት ሀሳቡ ከልቦናዉ ተገፎ እላዩ ላይ ለዉጦት የነበረዉ የተለየ ፀባይ ጠፍቷ የድሮዉ ፍፁም እየሆነ
"ፈጣሪ እስኪወስደኝ አልተዋትም "
ሲል በልቡ ቃል ገባ

ጌታቸዉ በጀብደኝነት የቤዛዊትን እርቃን ገላ እየዳሰሰ ከላይዋ ላይ ተነስቶ ወደ መሬት ወርዷ በድጋሜ ተመለከታት ልብሷን እንኳን ለመልበስ አልሞከረችም አይኖቿ ኮርኒሱ ላይ ተተክለዉ ደርቃ ቀርታለች እየተገላመጠ ሱሪዉን ለባብሶ ወደ ዉጪ ወጣ
ከደቂቃወች በኋላ ሲመለስ ቤዛዊት ሲወጣ እንዳያት አሁንም ደርቃለች ደስ አለዉ የሰራዉ ክፉ ስራ እነደማይጋለጥበት እረግጠኛ ሆነ
በመታመሟ ሊያዝንላት ሲገባ ተደሰተ በታመመች ልክና እራሷን ባልቻለች ወቅት ሁሉ የእሱ ሀጥያት ተደብቆ የሚቆይ የማይታወቅበት ስለመሰለዉ ተደሰተ
እርቃን ገላዋ አሁንም የተረገመ አይኑ ዉስጥ ስለገቡ እየተቻኮለ ሀጥያቱን ደገመዉ ሲጨርስ ቤዛዊትን ልብሷን አለባብሶ ከላይ ብርድ ልብስ ደርቦላት ምንም እንዳልተፈጠረ ወጥቶ ሊሄድ ሲል እማማ ስንቅነሽ ደረሱ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2👏1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_ዘጠኝ


#በክፍለማርያም

....እማማ ስንቅነሽ ደረሱበት
ቤዛዊት እዉነተኛዉ አለም ላይ አልነበረችም ህመሟ በሰራላት አለም ዉስጥ ሰምጣ ጠፍታለች አካሏ አልጋዉ ላይ ይጋደም እንጂ አይምሮዋ በትክክል እየሰራ አይደለም
አይኖቿ ኮሮኒሱ ላይ ተተክለዉ የምታስበው ባይታወቅም ተክዛ እሩቅ ሄዳለች የደፈረሱት አይኖቿ ግን መደፈሯን ያወቁ የጠረጠሩ ይመስል ያልፈሰሱ እንባወች አቅርረዋል የተንጨባረረዉ ፀጉሯ ትራሱ ያስጠላዉ ይመስል ተመነቃቅሮ ይታያል።

እማማ ስንቅነሽ የሆነ ነገር እንደተፈጠረ የጠረጠሩት የልጃቸዉ ፊት ላይ የመደናገጥ የመቻኮል የመቅበዝበዝ ምልክት እንዳዩ ነው።
"ምን አረካት አንተ አዉሬ"
ሲሉ ልጃቸዉ ላይ ጮሁበት
"ምንም ምንም"
እያለ እናቱን ገፍቷቸዉ ሊወጣ ሲል ቤዛዊት ከተኛችበት አልጋ ተነስታ ስትቆም ሁለቱም ዞረዉ አዩዋት
ቤዛዊት በቆመችበት አይኖቿን ወደ መሬት ልካ የምትፈልገዉ ነገር ያለ ይመስል ዙርያዋን ስታስስ ቆይታ ጥግ ላይ ከድስት አናት ላይ የተቀመጠ ማማሰያ አንስታ ወደ ጌታቸዉ በፍጥነት ተጠግታ ጌታቸዉን መምታት ጀመረች።

ጌታቸዉ
"ምን መሆኗ ነዉ ይቺ እብድ"
እያለ እራሱን ለመከላከል ፊቱን በእጆቹ ሲከላከል ቆይቶ ቤዛዊትን በሀይለኛ ጥፊ መሬት ላይ ጣላት
እማማ ስንቅነሽ የድረሱልኝ ጩሀት መጮህ ጀመሩ
"ልጄን ገደላት ድረሱልኝ
ልጄን ገደላት"
ጌታቸዉ እየተንጎማለለ በፍጥነት ቤቱን ለቆ ወጣ የእማማ ስንቅነሽንም ጩሀት ሰምቶ የመጣ ማንም ሰዉ አልነበረም።
እንደ እማማ አይነት መልካም ልብ ሲኖርህ ለልጄ ለዘመዴ እያልክ አትወግንም ለእዉነት ብቻ ነዉ የምትቆመዉ።

ጌታቸዉ ከዛን ቀን በኋላ ወደ ቤቱ አልተመለሰም ምን አልባት አደጋ ደርሶበት ሊሆን ይችላል
አልያ ስራ አጊንቶ ቀንቶት ሌላ ቦታ እየኖረ ከሆነ እንኳን ጤነኛ አይምሮ ኖሮት ይኖራል ብሎ ማመን ይከብዳል።
እማማ ስንቅነሽ እንግዳ የሆነች በህይወት የሌለች የልጃቸውን አምሳል የምትመስል ምስኪን ልጅ ይዘዉ ተሰቃዩ በየፀበሉ ፈጣሪን እየለመኑ መንከራተት ቤዛዊትን ከጉያቸዉ ሳይነጥሉ የጎረሱትን እያጎረሷት የጠጡትን እያጠጧት አብረዋት ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ።
እማማ ስንቅነሽ ቤዛዊትን በጠዋት ፀበል ይዘዋት ሄደዉ ወደ ቤት ሲመለሱ ቤዛዊት አልጋ ላይ ተቀምጣ በራሷ አለም እየዋኘች እማማ ስንቅነሽም ከጎኗ ተቀምጠዉ በሀሳብ ጭልጥ አሉ።
የቤዛዊት ነገር እያሳሰባቸዉ ነዉ ትንሽ ለዉጥ ስላላዩባት ፈጣሪን ማማረር እየጀመሩ ነዉ በዛላይ የሚላስ የሚቀመስ ነገር ቤት ዉስጥ የለም እጃቸዉ ደርቋል የሚረዳቸዉ ሰዉም ጠፍቷል
ከሀሳባቸዉ ሲባንኑ ወደ መሶቡ አምርተዉ ሲከፍቱት ባዶ መሆኑን አረጋገጡ
"ምን አረኩህ ፈጣሪ"
እያሉ ሲዞሩ ከታመመችዋ ከቤዛዊት አይን ጋር ተገጣጠሙ
እንደድሮ ጤነኛ በነበረች ሰአት እንደምታያቸዉ አይነት አስተያየት ስታያቸዉ ፀበሉ ለዉጥ እንዳለዉ ጠርጥረዉ ፊታቸዉ ላይ ፈገግታ እየተነበበ
"ጨርሰህ ማርልኝ አይ እኔ ማማረር ብቻ ሆነ ኑሮዬ ተመስገን"
እያሉ ወደ ቤዛዊት ቀርበዉ በእጃቸዉ ፊቷን ደበስበስ እያረጓት
"እራበሽ አደል ሆዴ ገዝቼ መጣሁ"
አሉና እያዘገሙ ወጡ ነገር ግን መግዣ ብር እንደሌላቸዉ ልባቸዉ ያዉቃል ጎረቤት ሁሌ መለመን ማስቸገር ታክቷቸዋል የማያዉቁትን ሰዉ ለመለመን ድፍረቱ ባይኖራቸዉም
ቤዛዊትን በረሀብ አልገላት ነገር እኔስ ብሞትም እድሜዬን ጨርሻለሁ እያሉ ለልመና ወደ ጎዳና መጡ።
"የሰዉ ፊት ለካ ዱላ ነዉ "
ጥቂት እጃቸዉን ዘርግተዉ እንደቆሙ ነገር ግን በአይኑ ገርመም አርጎ እያየ የሚያልፋቸዉ እንጂ ሳንቲም የሚሰጣቸዉ ጠፍቶ ሲተክዙ አንዲት ሴት የታሰረ ምግብ በፌስታል እያደለች እሳቸዉ ጋር ደረሳ እጇን ስትዘረጋላቸዉ እያመሰገኑ ተቀብለዋት
ቤት ዉስጥ ብቻዋን ጥለዋት ወደ ወጡት ወደ ቤዛዊት አመሩ።
የቤቱን በር ገፋ አርገዉት እንደገቡ የቤዛዊት ቦርሳ ተከፍቶ ዉስጡ ያሉት እቃወች መሬት ላይ ተበታትነዉ አዩ ቤዛዊት ግን አልነበረችም።

💫ይቀጥላል....💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስር


#በክፍለማርያም

...ቤዛዊት ግን አልነበረችም
ምግቡን መሶብ ዉስጥ አስቀምጠዉ ጉዋሮ ለጎዋሮ ቤዛዊትን አሰሷት ወደ ዉጪም ወጥተዉ አላፊ አግዳሚዉን ቤዛዊትን ያየ በማለት ጠየቁ ነገር ግን ቤዛዊት የዉሀ ሽታ ስለሆነች ወደ ቤታቸዉ በረንዳ ተመልሰዉ ተቀምጠዉ በነጠላቸዉ እያበሱት ነገር ግን የሚፈስ ድምፅ የሌለዉ የእዉነት እንባ ማንባት ጀመሩ።

ማልቀሱ ብቻዉን ግን ትርጉም እንደሌለዉ ሲገባቸዉ ቤዛዊትን ፍለጋ አስበዉ ሲቆሙ ቤዛዊት ከዉጪ እየገባች አጠገባቸዉ ቆመች
ፊቷ ላይ ደስታ ይነበባል ደረቷ እንደማበጥ ብሏል እማማ ስንቅነሽን በፍቅር አይን እያየቻቸዉ ደረቷ ዉስጥ የደበቀችዉን ብዛት ያለዉ ብር አዉጥታ ደንግጠዉ የቋሙት እማማ ስንቅነሽ እጅ ላይ አስቀመጠችዉ።

(ከደቂቃወች በፊት)
ቤዛዊት ከፀበል ስትወጣ ቅልል የሚል ስሜት እየተሰማት ነበር አይምሮዋም ሙሉ ለሙሉ ባይባልም እየስተካከለ ማሰብ ማገናዘብ እየጀመረች ነበር
ቤት ገብተዉ እማማ ስንቅነሽ በሀሳብ እርቀዉ ሲሄዱ አስተዋለቻቸዉ ባዶዉን መሶብ ሲከፍቱ እንደቸገራቸዉ ገባት ለዛም ነዉ አይን ላይን የተያዩት ገዥቼ መጣሁ ሲሏት ገንዘብ እንደሚያስፈልጋቸዉ አሰበች
እሳቸዉ እንደወጡ እስዋ ቦርሳዋን መፈለግ ጀመረች ዉስጡ ብር እንደሌለዉ ስታይ ተናደደች ነገር ግን የባንክ ደብተሯን ስላየችዉ እና ማዉጣት እንደምትችል ሲገባት እየተቻኮለች ወጣች"
አሁን
እማማ እጃቸዉ ላይ ያለዉን ብር እያዩ ደንግጠዉ እና ከየት አምጥታዉ ሊሆን እንደሚችል እያሰቡ
"ከየት አመጣሽዉ ልጄ"
አሏት
"የኔ ነዉ ከባንክ አዉጥቼዉ ነዉ"
አለቻቸው ደስታ ባዘለ ንግግር
አላመኗትም ተጠራጠሯት ከሰዉ ነጥቃ ቀምታ ያመጣች መስሏቸዉ ነበር እየተሻላት እንደመጣ ግን በንግግሯ በሁኔታዋ እያረጋገጡ ሲመጡ አምነዋት ተያይዘዉ ወደ ዉስጥ ገቡ።

እማማ ስንቅነሽ በቤዛዊት የጤና ለዉጥ ደስተኛ ሆነዋል ማስታመማቸዉን ፍቅራቸዉንም ሳይቀንሱ ከጎኗ ናቸዉ ቤዛዊትም ከቀን ወደ ቀን ፍፁም ጤነኛ እየሆነች ነዉ አስተሳሰቧም ወደ ጤነኝነት ተመልሷል
እማማ ቤዛዊትን ያገኟትን ቀን አስታወሱ እርቃኗን ብርድ ላይ መንገድ ጥግ ተቀምጣ ነበር ወደ ቤታቸዉ ሲመለሱ ያዩዋት በሩቁ ልብስ መስጠት ምግብም ማቀበል ይችሉ ነበር ነገር ግን ከመልካምነታቸዉ ባሻገር የሆነ ሀይልም አብሯቸዉ ነበር።
ለቤዛዊት መዳን ምክንያት ለመሆን ነበር የዛን ቀን ያገናኛቸዉ
አንዳንድ አጋጣሚዎች አጋጣሚ የሚታለፉ ነገሮች ብቻ አደሉም ምክንያትም ዉጤትም ሊሆኑ ይችላለ።

ቤዛዊት ጤናዋ እንደተመለሰ ወደ ፍፁም ጋር ሄዳ ብታስጠራዉም እሱ ማግኘት ስላልፈለገ ሳታየዉ ሳታገኘዉ ተመለሰች
እንደበፊቷ ለምን አላገኘኝም ስትልግን አይምሮዋን አላጨናነቀችም
አንዳንድ ነገሮች በጭንቀት እና በትግል አይፈቱም ጊዜ ያስፈልጋቸዋል
ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ስትመለስ ከባንክ ብር አዉጥታ ለቤት የሚያስፈልጉ በርካታ እቃወች ገዝታ ተመለሰች እሳቸዉም ጣፋጭ ምግብ እየሰሩ እየጠበቋት ነበር።
ምግቡ እስኪደርስ ለቤተሰቦቿ ስልክ ደወለች ድምፆን እንደሰሙ ድጋሜ ከሞት እንደተነሳች ቆጥረዋት በስልክ መሰማማት እስኪያቅታቸዉ ተጯጯሁ እናቷ እና እህቷ አሁን ካልመጣን ያለሽበትን ነገሪን ስላሏት ቤዛዊት የእማማ ስንቅነሽን ቤት አቅጣጫ ነግራቸዉ በደስታ ስልኩን ዘጋችዉ።
ከእማማ ስንቅነሽ ጋር ምግቡ ቀርቦ እየበሉ እማማ ማጉረስ ሲያበዙባት
"ጠገብኩ በአንድ ጉርሻ"
እያለቻቸዉ የማጥወልወል ስሜት ስለተሰማት ከገበታዉ ተነስታ እየተንደረደረች ማስታጠብያ ፈልጋ የጎረሰችዉን እንዳለ እየተፋች።
"ሆዴን ሳያመኝ አይቀርም"
አለች ትንሽ እንደ ቦርጭ ገፋ ያለዉን ሆዷን ዳበስ እያረገች
እማማ ስንቅነሽ ግን ልብ ብለዉ ሁኔታዋን ሲያስተዉሉት ነበር የሰዉነቷ ቅርፅ ለዉጥ ማስመለሷ ሁሉ ነገር ለቤዛዊት ባይገባትም እማማ ስንቅነሽ የቤዛዊት ማርገዝ ታዉቋቸዉ ነበረ።

ፍፁም ካለችዉ ሰዉ ይሁን ከተረገመዉ ልጃቸዉ ያወቁት ነገር ባይኖርም።

💫ይቀጥላል..💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍2🥰1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስራ_አንድ


#በክፍለማርያም

...ከማን ይሆን ብለዉ እየተጠራጠሩ
የቤዛዊት ቤተሰቦች ቤዛዊትን ፈልገዉ አስፈልገዉ ስላጧት ወደ ተስፋ መቁረጥ እየተጠጉ እናቷ ነጋ ጠባ ስታለቅስ ከቤት ወጥታ የጠፋች የታመመች ልጃቸዉ በድንገት ስትደዉል
ተአምር ነዉ የሆነባቸዉ
አባቷ ያለችበትን እንደሰሙ ከተቀመጡት ተነስተው ወደ ዉጪ በፍጥነት እየተራመዱ ወደ መኪናቸዉ አመሩ እናቷና እህቷ እየተደናገጡ እየተደሰቱም እኋላ ኋላ እያሉ ተከትለዋቸዉ መኪናው ዉስጥ ገብተዉ እንደተቀመጡ አባቷ መኪናዉን አስነስተዉ ወደ ቤዛዊት ገሰገሱ
የነገረቻቸዉ አካባቢ መኪናውን አቁመው ሁሉም ከመኪናዉ ወርደዉ የታመመች የተጎሳቆለች ወጣት ሴት እየጠበቁ ቤዛዊት የእማማ ስንቅህን የቆየ ቀሚስ ለብሳ ደንዳና ሴት ወይዘሮ መስላ ፊቷ እንደ ልጅነቷ ብርሀን እየፈነጠቀ ፊት ለፊታቸዉ ደርሳ ቆመች
እናቷ እንባ እያነቡ እላይዋ ላይ ተጠመጠሙባት
"ምን ነዉ ልጄ ምን በደልኩሽ"
እንባቸው እየወረደ ነው
"አረ ምንም አረ ምንም "
ትላለች ቤዛዊት የእናቷ ማልቀስ እሷንም ሆድ እያስባሳት ማልቀስ ጀምራ
እናቷ ለደቂቃወች አቅፈዋት ቆይተዉ ሲለቋት ታላቅ እህቷ በተራዋ አቀፈቻት
"ደህና ነሽ አደል ቤዚ"
የታናሽ እህቷን ጉንጭ እየሳመች
ቤዛዊት እህቷን ትጠላት እንደነበር ከአይምሮዋ ስላልተደበቀ
"ይቅርታ አርጊልኝ"
እያለች ታላቅ እህቷን ለመነቻት
"ምንም አደል አንቺ ብቻ እንኳን ሰላም ሆንሽ"
ስትል ታላቅ እህቷ የቤዛዊትን ጉንጮች መሳም ጀመረች።

አባቷ ሁሉንም እጃቸውን አጣምረዉ ሲመለከቱ ቆይተዉ
"መቼም ከዚህ በኋላ ህፃን አደለሽም በምርጫሽ አልገባም"
እያሉ ሊያቅፏት ተጠጉ
አንዳንዴ ነገሮች ከተበላሹ በኋላ ሰዉ ሊረዳን ሊያግዘን ይሞክራል በወቅቱ ግን አይደርስልንም

ፍፁም ሳይታሰር አባቷ ፍላጓቷን ቢያከብሩላት ይሄ ሁሉ ባልተፈጠረ
አባቷ እጇን ይዘዉ ወደ መኪናዉ ሊያስገቧት ሲሉ ቤዛዊት
"ሁለተኛዋ እናቴን ላስተዋዉቃችሁ
እያለች ወደ እማማ ስንቅነሽ ቤት ይዛቸዉ ገባች።

"እሳቸዉ ናቸዉ ለዚህ ያበቁኝ"
ስትል አንድ በአንድ እማማ ስንቅነሽን ለቤተሰቧቿ ማስተዋወቅ ጀመረች።
እማማ ስንቅነሽ በነደፈ ነጠላቸዉ ሸፍነዋታል ቁራሽ ዳቦ አካፍለዋታል በእድሜዋ ሙሉ ከፍላ የማታገኘዉ ደግነት ሰጥተዋታል ቤዛዊትም ጥላቸዉ መሄድ ስታስብ ዉስጧ ቅር እየተሰኘ እማማ ስንቅነሽን
"እኛ ቤት አብረን እንሂድ እንከባከቦታለሁ"
ስትል በስስት አይን እያየቻቸዉ
በመሀል በሀሳብ ጭልጥ ብለዉ የጠፉት የቤዛዊት መለወጥ ጤናዋ መመለሱ ያስገረማቸዉ አባቷም
"እባኮን እሺ ይበሏት ለኛም እናት ይሆኑናል ሸክም እሆንባችሁዋለሁ ብለዉ አያስቡ"
ብለዉ ጨመሩበት
እማማ ስንቅነሽ በሞጨሞጮ አይናቸዉ ቤታቸዉን እየቃኙት ሲያስቡ ቆይተዉ
"ምን አረኩልሽና ዉለታ ዋሉልኝ ብለሽ አታስቢ የሰማይ መግቢያዬን እያደላደልኩ ነዉ"
ብለዉ በነጠላቸዉ አይናቸዉ አካባቢ ዳበስ እያረጉ
"ስትችይ እኔም ስለምትናፍቂኝ እየመጣሽ እይኝ "
አሉና መምጣት እንደማይችሉ በሚገልፅ አኳሀን አንገታቸዉን አቀርቅረዉ ቀሩ።
በልባቸዉ ልጃቸዉ ዉልብ እያለችባቸዉ ላለማሰብ እየታገሉ ቤቱ ዉስጥ የነበሩት ሁሉ በሀዘን ተነክቶ ቤቱ በዝምታ ተዋጠ
በመሀል እማማ ስንቅነሽ ተነስተዉ ቆመዉ
"ምግብ ላቅርብ በልታችሁ ሂዱ"
አሉ ፊታቸዉ ላይ የፈገግታ ምልክት እየታየ
"ልጃችሁ ከሰዉ እኩል አርጋኛለች"
ሲሉ ከባንክ አዉጥታ የሰጠቻቸዉን ብርና ያሞላችላቸዉን የቤት ቁሳቁስ አስበዉ ቤዛዊትን እያመሰገኗት
ቤዛዊት እማማ ስንቅነሽን ስማ ተሰናብታቸዉ ወደ መኪና ዉስጥ ስትገባ እየመጣች ልትጠይቃቸዉ ቃል ገብታ ነበር።
መኪናዉ ተነስቶ መንቀሳቀስ ሲጀምር እማማ ስንቅነሽ በጭላንጭሉ አይናቸዉ መኪናዉን እያዩ ተክዘዉ ቀሩ መኪናዉ እርቆ ሄዶም በሀዘን ተዉጠዉ ቆመዉ እያሰቡ ነዉ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በክፍለማርያም

... እያሰቡ ቆመዉ ቀሩ
ቤዛዊት ቤቷ ገብታ እንደ ቀድሞዉ ህይወቷን መምራት ጀምራለች ፍፁም ትዉስ እያላት ታስበዉና ትንሽ ይረጋጋ ብላ መሄዱን መጠየቁን ትተወዋለች ነጋ ጠባ ግን ሳታስበዉ ዉላም አድራም አታዉቅም።

በመሀል ግን ምግብ አልስማማ ሰዉነቷ በተለይ ሆዷ ከፍ ማለት ሲጀምር
"አርግዤ ይሆን"
እያለች መጠራጠር ጀመረች
"እንዴት"
እያለች እራሷን መጠየቅ ጀምራ ጥርጣሬዋ እየጎላ ሲመጣ ለመመርመር ወደ ሀኪም ቤት ተደብቃ ከቤት ወጣች።
ሀኪም ቤቱ ዉስጥ ካርድ አዉጥታ አግዳሚ ወንበር ላይ እንደተቀመጠች እናቱ ላይ ታቅፎ የተቀመጠ ህፃን ስታይ የልጁ ዉኔታ አስደስቷት ለማጫወት እጆቿን እያንቀሳቀሰች በፊቷ የተለያየ ገፅታ እየታየ እሷም አብራዉ ቆይታ ስሟ ስለተጠራ ወደ ዉስጥ ገባች።

ፍፁም ጨላማ ቤት ተብሎ ከሚጠራዉ ቤት ሲወጣ ፀባዩ ተስተካክሎ የበፊቱን ፍፁም መስሎ ነበር
የሟጠጠ ተስፋን ወደ እዉነተኛ ተስፋ ቀይሮ እስሩን ለመቀጠል እና አይምሮዉ ዉስጥ ያሉ መጥፎ ተዝታወቹን ሁሉ እረስቶ እንደሌሉ ቆጥሯቸዉ ወደ ቀድሞዉ ክፍል ተመለሰ
የእስር ህይወት ተመሳሳይ ተደጋጋሚ ቢሆንም ፍፁም ጠዋት ተነስቶ ለጤናዉ ይንቀሳቀሳል
ሲመለስ ወረቀቱ ላይ ሀሳቦቹን ይፅፋል አዘዉትሮ ግን መፅፍትን ላይብረሪ እየገባ ሲያነብ ይዉላል
ቤዛዊትን ሲያስታዉስ ምሽቱ ይገፋለታል መጨረሻ ቀን በተናገራት ንግግር ተከፍቶ ልትጠይቀዉ ዳግም ብትመጣ እያለ መመኘት ጀምሯል ከሱ ስም ጋር የሚመሳሰል ሰው
"ዘመድ ሊጠይቅህ መጥቷል"
ሲባል ጆሮወቹ ይሾላሉ የሱ አለመሆኑን ሲያዉቅ አንገቱን ደፍቶ ቤዛዊት እንድትመጣ ይፀልያል።
አንዳንዴ ቤዛዊት የሱ ሳትሆን የሌላ እቅፍ ዉስጥ የሌላ ፍቅር ዉስጥ ስትገባ በሀሳቡ ይስልና
ይበሳጫል እራሱን ይወቅሳል ሲረጋጋና ነገሩን አጢኖ ሲመለከተዉ ደሞ የእሷን ደስታ ብቻ ይመኛል
"እኔ ከታሰርኩ እሷ ቆማ ትቅር ማለት አይገባም"
ይልና ጥጉን ይዞ አርፎ ይቀመጣል
ፎጣ አናቱ ላይ ከሚያረገዉ ከተደባደበዉ ማስረሻ ጋም ስለታረቁ አብረዉ ስላሳለፉት ህይወት እያወሩ ቀኑ ይመሻል

ቤዛዊት ምርመራዋን አጠናቃ ዉጤት ለመስማት ዶክተሩ ፊት ተቀምጣለች
"እንዴት ነሽ ቤዛዊት"
አላት በእድሜ ገፋ ያለዉ ዶክተር አይኖቹ ላይ የነበረዉን መነፅር እያወለቀ
"ደህና ነኝ"
አለችዉ ቤዛዊት እንደማፈር እያለች
"በምርመራዉ ሆድሽ ዉስጥ የአንድ ወር ከ ሰባት ቀን ፅንስ እንዳለ ተረድተናል"
ቤዛዊት ዶክተሩ ደንግጣ አየችዉ
"ስንት ወር አልከኝ?"
ደገመላት
"ወር ከሰባት ቀን እኛ ጋር ክትትል ማረግ መጀመር አለብሽ..."
ቤዛዊት አልሰማችዉም ጣቶቿን እያንቀሳቀሰች መቁጠር ጀመረች
የፍፁም ቤት ከፍፁም ጋር ያሳለፉት የፍቅር ምሽት ተዝ እያላት ወደ ዛን ቀን በሀሳብ ተጉዛ የፍፁም ክንድን ተንተርሳ ደረቱ ላይ ተኝታ ፀጉሯን በእጆቹ እየደባበሰ እወድሻለሁ ያላት አየታወሳት
"አንድ ወር አንድ ወር ..ፈጣሪዬ "
አለችና ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ በደስታ ተነስታ ቆመች
"ቤዛዊት ችግር አለ"
እያላት ዶክተሩም ተነስቶ ቆሞ
"የፍፁም ልጅ ነዉ ዘሩን ሰጥቶኝ ነዉ የሄደዉ"
ዶክተሩን በደስታ አቅፈችዉ የተደናገጠዉ ዶክተር በግድየለሽነት ታቀፈላት ወድያዉ ያቀፈችዉን የማታዉቀዉን እየለቀቀችዉ
"እመለሳለሁ እመጣለሁ..."
እያለች ፍፁምን አግኝታ የደስደሱን ለመንገር እየተጣድፋ ወጣች

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስራ_አራት


#በክፍለማርያም

...እየተጣደፈች ወጣች
መንገድ ላይ በደስታ ብዛት ፊቷ ላይ ጤነኛ የሆነ ፈገግታ እየታየባት ወደ ማረምያ ቤቱ ከመግባቷ በፊት ከለመደችዉ ምግብ ቤት ምግብ አስቋጥራ
አዲስ ህይወት አዲስ ጅማሬ እንዳገኘ ሰዉ መንፈሷ ብሩህ ሆኖ ስትከንፍ ደርሳ ፍፁምን አስጠርታዉ በሽቦ በታጠረዉ ክልል አሻግራ የፍፁምንን መምጣት መጠባበቅ ጀመረች።

ፍፁም የጀመረዉን የህይወቱን መፅሀፍ እየፃፈ የእሱ መታሰር ከቤዛዊት በአካል እርቋ ተስፋዉ ጨልሞ ፍቅራቸዉ ያሰበዉ ሳይሆን በጅምር ቀርቶ እሱም እሷም በየራሳቸዉ መንገድ ላይ ተራርቀዉ መቅረታቸዉን ፅፎ እስከዛሬ ቀን ያለዉን የህይወቱን ምስቅልቅል ወረቀቱ ላይ ካሰፈረ በኋላ ወደ ፊት የሚፈጠረዉ ስለማይታወቅ የታሪኩን ፍፃሜ ገና እያየ የሚቀጥለዉ ስለሆነ
በተቀመጠበት እየተከዘ የስሙን መጠራት ገና እንደሰማ ተስፈንጥሮ ቆሞ በደስታ ልቡ ጮቤ እየረገጠ እየጨፈረ መራመድ ጀመረ።

ከቤዛዊት ዉጪ ማንም ሊጠይቀዉ እንደማይመጣ ልቡ ስለዋቀዉ ነዉ መደሰቱ
ካስከፋት ቀን ጀምሮ የእሷን መምጣል በጉጉት በልመና ሲጠብቅ ስለነበር
አይኖቿ እየናፈቁት አየተደሰተ ወደ ዘመድ መጠየቅያዉ ስፍራ ደረሰ።
አይን ለአይን በርቀት ሲተያዩ ሁለቱም ፊት ላይ ብልጭ ብሎ የጠፋ ፈገግታ ታየ
አይናቸዉ ሳይነቀል ተጠጋጉ በተወሰነ እርቀት ተጠጋግተዉ አቅራቢያቸዉ ያለች የማረምያ ቤቱ ፖሊስ ቤዛዊት የያዘችዉን ምግብ ለፍፁም ጎርሳ እንድታቀብለዉ በማንክያ ውስጡን ነካ ነካ ካረገች በኋላ ነገረቻት ቤዛዊት መጠነኛ ጉርሻ በአፍዋ እያኘከች
"እንዴት ነህ ፍፄ"
እያለች ምግቡን አቀበለችዉ አፏ ላይ የያዘችዉ ምግብ አላስወራ ስላላት ተረጋግታ አኝካ እዋጠችዉ
ፍፁም በደስታና በፍቅር እያያት ነበር ፊቷ ላይ የማይነበብ ፍፁም ሰላም ይነበብባታል ጤናዋ እንደተስተካከለ ገምቶ በልቡ ተመስጌን እያለ የአፍ አመል ስለሆነ
"ደህና ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?"
ተነፋፍቀዋል መሀላቸዉ ላይ ግን የሚያስተያይ ነገር ግን የማያገኛኝ አጥር አለ
እስርም እንደዚህ ነዉ
"ልጅ ልወልድልህ ነዉ"
እያለች እጆቿን ወደ ሆዷ ሰዳቸዉ ሆዷን በቀስታ መዳበስ ጀመረች
ፍፁም መልስ ሳይሰጣት አብረዉ ያደሩበትን ቀን አስታወሰ ተሽሎት ከሆስፒታል የወጣቀን
አሰላዉ አንድ ወር ከሳምንት አካባቢ
"እርግጠኛ ነሽ ሀኪም ቤት ሄደሽ ነበር? "
ጠየቃት በማመን እና ባለ ማመን መሀል ባለ ግር የማለት ስሜት ዉስጥ ሆኖ
ቤዛዊት ፊቷን ከላይ ወደ ታች እየነቀነቀች
"አዎ የአንድ ወር ከሰባት ቀን ልጅ ሆዴ ዉስጥ አለ"
ፍፁም ጥርጣሬዉ እነደጉም በኖ ጠፋ በቤዛዊት እና በእሱ አንድ አምሳል እንዳለ ልቡ አሰየነገረዉ ፊቱ በደስታ እየፈካ ጣቶቹን በአጥሩ ላይ እደገፈ ባይነካኩም እሷም በሱ ትይዩ እጆቿን ዘረጋች
"እወድሻለሁ "
ሲል በቀስታ አወራ
"እኔም እወድሃለሁ "
የእሷ ድምፅ ከሱ በጣም ቀንሶ በዉስጡ አብረሀኝ ከጎኔ ብትሆን ልጃችንን አብረን እናሳድግ የሚል አስተያየት አብሮት ነበረ።

💫ይቀጥላል 💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስራ_አምስት


#በክፍለማርያም

...አብረን እናሳድግ በሚል አስተያየት
ቤዛዊት እና ፍፁም ለደቂቃዎች ቃላት ሳያወጡ ማሃላቸዉ ባለዉ ሽቦ በአይኖቻቸው እየተያዩ ነገር ግን ሁለቱም ልቦቻቸዉ ተጨንቀዉ ሀዘን የተበረዘበት ፍንጣቂ ደስታን ተሸክመዉ በአይኖቻቸዉ ፍቅርን አብሮ መሆንን ተርበዉ ጥቂት ከተያዩ በኋላ
"ልጃችንን ወልጄ በፍቅር አሳድገዋለሁ"
ቤዛዊት ይሄን ስታወራ የእንባ ሳግ አፍዋ ዉስጥ እንቅ እያረጋት ለማልቀስ እያኮበኮበች ነበር
ፍፁም ከእስር የመፈቻ ጊዜዉ በጣም እሩቅ ስለሆነ ያለእሱ የምታሳለፍቻዉ አመታት እየታያት
በተለይ ያ ጠይም መጀመርያ የትምህርት ቤቱ በር ላይ አይታዉ ደስ ብሏት ሰአት የጠየቀችዉ
ነገሮችን ያስተማራት የመከራት ህመሟን ችሎ እያስታመማት ስታጠፋ ስትበድለዉ ከጎኗ ያልራቃት ሁሉ ነገሯ የሆነዉ ፍፁም በእሷ ህይወት በተያያዘ ጉዳይ በድንገተኛ ፀብ የሰዉ ነብስ አጥፍቶ ለእስር ተዳርጎ ፊት ለፊቷ ቆሞ ስታየዉ ልጅ ከእሱ ማርገዟን የደስታ ዜና ይዛ እንኳን ደስታዋ ሙሉ ሊሆን አልቻለላትም
የሆነ የጎደለ ነገር እንዳለ ልቦናዋ ያዉቀዋል የጎደለዉ
ፊት ለፊቷ የቆመዉ የቀድሞዉ አስተማሪ ፍፁም ደምሴ ነበር።

"የምታለቅሺ ከሆነ እቀየምሻለሁ"
ፍፁም ቆጣ ሲልባት ማልቀሷን ተወችዉ
ከቤዛዊት ጋር እንደተለያየ ፍፁም ልጁን መዉለዷ መልካም ነዉ ወይ ሲል እራሱን ጠየቀ
ባትወልደዉ እና ወደ ፊት ሌላ ጥሩ አሳቢ መልካም ባል አግብታ ከእሱ ብትወልድ እያለ አስቦ ነበር ቤዛዊት ወልጄ በፍቅር አሳድገዋለሁ ያለችውን ሲያስታዉስ ሀሳቡን በምንም ተአምር እንደማትቀበለዉ ሲገባዉ ያሻዋን ታርግ ሲል ማሰቡን እርግፍ አርጎ ተወዉ።

መታሰር ከማሰብ ባያግድም ከተግባር ግን ስለሚያግድ ከጎኗ ሆኖ ምንም ሊያረግላት ስለማይችል ለመምከር ይሞክራል እንጂ እሷ የፈቀደችዉን ሁሉ እንድታረግ ከልቡ ፈቅዶላት ነበር
ቤዛዊት ፍፁምን ጠይቃዉ እየተመለሰች መንገድ ላይ ለፍፁም የነገረችዉን የምስራች ለቤተሰቦቿም መናገር እንዳለባት ገምታ የሚሰጡዋትን መልስ ለመስማት ጉዋጉታ ወደ ቤቷ አመረች ።

ቤት ዉስጥ ሁሉም ተሰብስበዉ ምግብ ቀርቦ ከተመገቡ በኋላ ማእዱ ተነስቶ ቡና ለመጠጣት አየጠበቁ ቤዛዊት
"የምነግራችሁ ትልቅ ጉዳይ አለ"
የሁሉም ሰዉ ጆሮ እና ቀልብ እሷ ላይ አረፈ።
ቤዛዊት በሽታዋ የተነሳባት አሁን ደሞ ምን ልትለን ይሆን እያሉ ነበር ቤተሰቦቿ
ቤዛዊት ወሬዉን ከመጀመሯ በፊት ኮስታራዉን አባቷን በቀስታ አይታቸዉ
"ይሄን የምነግራችሁ እናንተ የኔ የምወዳችሁ ቤተሰቦቼ ስለሆናችሁ ስለማከብራችሁም ነዉ
ነገር ግን የራሴን ዉሳኔ እንድትጋፉኝ አልፈልግም.."
ትንፋሽ ለመሳብ ንግግሯን ገታ አረገች
እናት እና አባቷ እየተያዩ ነበር ቀጥላ የምትለዉ ለመስማት ወደ ዋና ሀሳቧ እንድትገባ አስበዉ ምን ልትላቸዉ እንደ ሆነ ለመገመት እንኳን ስላልቻሉ ታላቅ እህቷ ከተቀመጠችበት ተነስታ ከቤዛዊት አጠገብ ቆማ እህቷን እያቀፈቻት
"ምን ለመናገር ፈልገሽ ነዉ ምንም ይሁን ግን እኔ ሁሌም ከጎንሽ አለሁ"
ድጋፏን አቅፋ ገለፀችላት
ቤዛዊት ካቆመችበት አንገቷን ወደ መሬት አቀርቅራ
"እኔና ፍፁም ልጅ ልንወልድ ነዉ"
ይህንን እንዳለች አባቷ ከተቀመጡበት ተነስተዉ ቆመዉ
"እየቀለድሽ መሆን አለበት ከነብሰ ገዳይ አርግዣለሁ እያልሽን ባልሆነ"
የፌዝ ሳቅ እየሳቁ
ቤዛዊት ካቀረቀረችበት አንገቷን ቀና እያረገች አባቷን እያየቻቸዉ
"አባ አብጄ ታምሜ እኔን ማየት ካልወደድክ የኔን ተስፋ የኔን ፍላጓትን ለማሙዋላት ምን
የሚይዝህ ነገር አለ ነዉ የኔ ሀዘን እንጂ ደስታዬ ትርጉም አይሰጥህም"
ቤዛዊት አባቷን እንዴት ታስረዳቸዉ በምንም ሊረዷት አይችሉም በቆመችበት ልብሶቿን እያወላለቀች
"ይሄ ከሆነ የሚያስደስትህ ኡ ኡ እያልኩ ከዚህ ቤት አወጣለሁ"
ቤዛዊት ሆን ብላ የአባቷን ልብ ለማየት ነበር ይሄንን ማረግ የጀመረችዉ ያሰበችዉም ተሳካላት አባቷ ልብስ እያወላለቀች ሲያይዋት ተጠግተዉ ያወለቀችዉን ልብስ እንድትለብስ እየረዷት
"ያንቺን ደስታ እነጂ ሀዘንሽን መቼም አስቤ አላዉቅም"
ሲሏት ቤዛዊት የጀመሩትን ወሬ ሳታስጨርስ አቀፈቻቸዉ።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስራ_ስድስት


#በክፍለማርያም

...አቀፈቻቸዉ
እናቷ መቼም ቢሆን የእሷን ፍላጎት ተጋፍተዉ ባያዉቁም ትምህርትን ሳትመረቅ ልጅ ለመዉለድ በመቸኮሏ ቅር ቢሰኙም አጣሁዋት አይምሮዋ ተቃዉሶ ተቀጨችብኝ ብለዉ ካዘኑበት በርካታ አመታት ጤናዋ ተመልሶ ከፊታቸዉ ቆማ የልጅ ልጅ ላሳያችሁ ነው ማለቷ ለእሳቸዉ አለም ነበር
የሚያስጨንቃቸዉ ሁሌ የልጃቸዉ ጤንነት ብቻ ስለነበር።

ትምህርት ስራ ገንዘብ ሀብት ....የህይወት መስመሮች ዉስጥ ያሉ መንገዶች ሊሆኑ ይችላሉ
ዋናዉ የህይወት ዋስትናችን ግን ጤንነታችን ላይ የተመረኮዘ ነዉ።
የቤዛዊት ሆድ ከቀን ወደ ቀን እየገፋ ፍፁም ጋር በየሳምንቱ ሳትቀር የሚያስፈልገዉን ይዛ እየጠየቀችዉ የመዉለጃዋ ስዓት ሲቃረብ የህመም ስሜትም ጀመራት።

በበፊቱ የአይምሮ ህመሟ ወቅት እሷ ሳይታወቃት ስትወድቅ ስትነሳ ሰዉነቷ ልጁን ለመቋቋም አልቻለም ነበር
ሆድዋ አካባቢ ቀላል የህመም ስሜትን እየተሰማት መራመድም እያቃታት ፍፁምን መጠየቅ እየፈለገች ነገር ግን ከአቅሟ በላይ ስለሆነ ቤት ዉስጥ እራሱ ጉድ ጉድ ማለቱ ሲያቅታት ቤተሰቧቿ ወደ ሆስፒታል ወሰዷት።

የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ሆና ቤዛዊት እህቷን
"ወረቀት እና እስኪርቢቶ አቀብይኝ"
አለቻት
"ምን ልትፅፊ ነው ደሞ"
እያለች እስኪርቢቶ ከቦርሳዋ አዉጥታ ወረቀት ስላጣች
"ወረቀት ግን የለኝም ቤዚ"
ቤዛዊት ፊት ላይ እርግዝናዉ ይሆን ባልታወቀ ሁኔታ ተለዋዉጣለች ጉንጮቿ ቀልተዋል የአይኖቿ
ቆቦች ወፍረዉ አይኗን መግለጥ ያቃታት ነዉ የምትመስለዉ
"ለፍፁም የምፅፍለት ነገር ነበር ተይዉ በቃ ልጄን ወልጄ አንድ ላይ ከልጄ ጋር ስንሄድ እነግረዋለሁ"
አለችና በትግል ለመሳቅ እየሞከረች
"የልጄን ስም ዳግማዊት ፍፁም ብላትስ"
እህቷን እየጠየቀቻት የእንሽርት ዉሀዋ ፈሰሰ።
የማዋለጃ ክፍል ዉስጥ ሀኪሞቹ ቤዛዊትን ለማዋለድ ጥረት እያረጉ ነዉ
ቤተሰቦቿ በረንዳ ላይ ሆነዉ በጭንቀት የልጃቸውን ሁኔታ ለማወቅ ከወድያ ወዲህ ይንጓማለላሉ
ቤዛዊት የምጥ ጩሀት ተጮሀለች
"ኡ ኡፍ ኡ ኡ "
ጩሀቷን ዉጪ የሚሰሙት እናቷ መቆም ስላልቻሉ አንጀታቸዉን እስር አርገዉ ተቀመጡ
አባቷ በሀሳብ ጭልጥ ብለዉ ሄደዋል እህቷ በፍርሀት እርዳለች የቤዛዊት ሁኔታ አወራሯ አልጣማትም ነበር።
ፍፁም በየሳምንቱ መምጣት አስለምዳዉ ስትቀር ቅር ያለዉ ቢሆንም የሆዷን መግፋት
የመዉለጃዋ ቀይ እየደረሰ ስለመጣ
እየተጨነቀም ቢሆን ልጁን አቅፋ መጥታ እንደምታሳየዉ ተስፋ እያደረገ ነበር።
ዶክተሮቹ እንድትበረታ እየነገሯት ነው ኦፕራሲዮን ማረግ የፈሩ ይመስላሉ
ቤዛዊት ለመጨረሻ ጊዜ ስትጮህ ከሆዷ አዲስ ሰዉ አዲስ ፍጥረት ወደ አለም ቀላቅላ
በዛችዉ ቅፅበት የእሷ ህይወት ግን ከዚህ አለም ሾልኮ ሄዶ በድን ሆና ነበር

(ከደቂቃዎች በፊት)
ቤዛዊት በአልጋ እየተገፋች ወደ ማዋለጃ ክፍል ከመግባቷ በፊት
በተኛችበት ሆና ቀና ማለት እየከበዳት ከርታታ አይኗን ለመግለጥ እየታገለች ቤተሰቦቿን ተሰብስበዉ ለአፍታ አየቻቸዉ እናቷ እየሮጡ የሚገፋዉ አልጋ ላይ ደርሰዉ እጇን ለመሳም ሲሞክሩ ቤዛዊት ቃል ከአፏ አወጣች
"ልጄን አደራ ልጄን አ ደ ራ"
ሁሉ ነገር የታያት ይመስል ነበር።

የመጨረሻውን ክፍል ነገ 12 ሰዓት ይጠብቁ

💫ይቀጥላል 💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
#ህመም_ያዘለ_ፍቅር


#ክፍል_አስራ_ሰባት(የመጨረሻ ክፍል)

#በክፍለማርያም

..ልጄን አደራ እያለች ነበር
ፍፁም እስር ቤት ዉስጥ የቤዛዊትን ልጃቸዉን አቅፋ መምጣት በጉጉት ይጠብቃል ነገር ግን ቤዛዊትን በላሁ የሚል ጅብ አልጮህ አለ።

የቤዛዊት ቀብር ተፈፅሞ ልጇን ቤዛዊት ባወጣችላት ስም አየጠሩ ቤተሰቦቿ በከባድ ሀዘን ዉስጥ ሆነዉም ቢሆን በእሷ ምትክ ልጅ ሰጥታቸዉ አልፋለች እና የወለደቻትን ቆንጅዬ ሴት ልጅ እንደቤዛዊት አይተዉ እየተንከባከቧት ነበር።

እስር ቤት ቀን ወራት ነዉ አመት ዘመን ነዉ ደቂቃ እየተንቀራፈፉ ነዉ የሚጓዙት ፍፁም ጥግ ላይ ተቀምጦ ወረቀት እና እስኪቢርቶዉን ይዞ
የህይወቱን የመጨረሻ ክፍል በመፃፍ ላይ ነዉ
ቤዛዊት ምን ገጥሟት ቀረች ለሚለዉ መልስ እንኳን መልስ ማግኘት አልቻለም በልቡ ቤተሰቦቿ አስገድደዋት ልጁን አስወርዳ ሌላ ባል አግብታ ይስላል
እስር ቤቱ ዉስጥ የመጀመርያዎቹ ሳምንታት ቤዛዊት
"የምስራች ልጅ ልወልድልህ ነዉ"
ብላዉ የጠፋችበት ወቅት ለእሱ ከባድ ነበር ስሙ የተጠራ እየመሰለዉ በለሊት
"አቤት"
ይል ነበር አንዳንዴ ቤዛዊት ያስጠራችዉ እየመሰለዉ
በህልሙ ሁሌ ልጇን አቅፋ እየሳቀች ትቀርበዉና አጠገቡ ስትደርስ የዉሀ ሽታ ሆና እንደጉም ትበተናለች ይጨነቅ ይረበሽ ነበር።
ሰከንዶች እያዘገሙ ደቂቃ ይሆናሉ ደቂቃወች ወደ ሰአት ለማደግ ይንቀራፈፋሉ ሰአታት ሰአት ሆነዉ ለመቆጠር አቅም ያንሳቸዋል ቀን እና ለሊት ለመለዋወጥ በጣም አሰልቺ ጊዜን የሚወስዱ እየመሰለው ቀን በመቁጠር ተጠምዶ ሲዉል ነበር።

አመት አመትን እየተካ ፍፁምም የወጣትነት ፊቱ በጎልማሳ ፊት እየተቀየረ የጭንቀት ሀሳቦቹ ቀስ በቀስ እየቀለሉት
ቀን መቁጠሩን ትቶ የተፈረደበትን ብዙ አመታትን ወደማገባደዱ ሲደርስ ጭንቀቱ ዳግም ማገርሸት ጀመረ።

ፍፁም እድሜዉ ወደ ሀምሳወቹ እየተጠጋ ነዉ መፈቻዉ እየደረሰ ሲመጣ ወደ በፊቱ ሀሳብ ተመለሰ
"ፍቅር አያረጅም ትዝታ አያረጅም
እድሜ ቢጠወልግ ሰውነት ቢጃጅም"
ቤዛዊት እሱን ለመጠየቅ መጥታ ልጅ አርግዤልሀለዉ ያለችዉን ቀን እያስታወሰ አሁን ቤዛዊት እና ልጁ ሊኖሩ የሚችሉበትን ሁኔታ እያሰበ ይቆዝም ገባ።
የቤዛዊት ቤተሰቦች ለፍፁም ልጁን ለማሳየት ማረምያ ቤት ለመምጣት ያስቡና የተፈረደበት ፍርድ ብዙ አመታት መሆኑን ሲያዉቁ ልፋት እና ልጅቷን ማንከራተት እየመሰላቸዉ ጥቂት ጊዜያት በተግባር ባያረጉትም ያስቡት ነበር
አመት እየተለወጠ በአመት ሲተካ እረሱት የቤዛዊት አባትም በህመም ተይዘዉ ብዙም ሳይቆዩ ስለሞቱ እህቷ ባል አግብታ የራሷን ሁለት ልጆች ወልዳ ከእናቷ ጋር የቤዛዊትን ልጅም ጭምር ፍቅር ሰጥተዉ እየተንከባከቧት አሳደጓት እድሜዋም ወደ ሀያወቹ እየተጠጋ ወጣት ሆናለች
ፍፁም የመፈቻ ስሙ ተጠርቶ የነበረውን ሁሉ ታሪኩን ከፃፈበት ወረቀት ዉጪ ሁሉንም ለታሳሪወች አከፋፍሎ ሁሉንም አቅፎ ተሰናብቶ ከማረምያ ቤቱ ወጣ
የብዙ አመት መኖርያ የነበረዉን እስርቤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ተመልክቶት ግቢዉን ለቆ ወደ ቤዛዊት እና ልጁ ገሰገሰ።

የእነ ቤዛዊት በር ጋር ደርሶ ቆመ በር ማንኳኳት አልቻለም ቆሞ ልቡ ሲመታ እና ሲጨንቀዉ የግቢያቸዉን በር ተደግፎ ለመረጋጋት እየሞከረ በሩ ተከፍቶ ወጣት ሴት ወጥታ
"ምን ሆነዉ ነዉ አሞት ነዉ ዉሀ ላምጣሎት?"
ፍፁም አንገቱን ቀና አርጓ አያት የቤዛዊትን አይን የያዘች ደግነቷም እንደሷ የሆነ ቆንጆ ልጅ
ልቡ ልጁ እንደሆነች እየነገረዉ የጥንቱ ፈገግታ ፊቱ ላይ ባይኖርም ለመሳቅ እየታገለ
"ስምሽ ማነዉ?"
ብሎ ጠየቃት
ደንግጣ የፍፁምን የተዳከመ የከፋዉ የሚመስል ፊት ለአፍታ አይታ
"ዳግማዊት"
አለችዉ
"የአባትሽን ስምም ንገሪኝ"
ፍፁም መጀመርያ የቤዛዊትን ስም ሲጠይቃትም እንደዚህ ነበር ያላት
ዳግማዊት ማን ነዉ ምን ፈልጎ ነዉ...በሚል የጥርጣሬ አይን እያየችዉ
"ዳግማዊት ፍፁም"
እያለችዉ አያቷ
"ከማን ጋር ነዉ ደሞ የምታወሪዉ"
እያሉ ወደ ደጅ ሲወጡ አብራዉ የቆመችዉን ሰዉዬ ተመለከቱት እርጅናዉ በርቀት አላሳይ እያለ ስለሚያስቸግራቸዉ በጣም ቀርበዉ ተጠግተዉ እያዩት
"ማን ነህ አንተ"
ፊቱ ዉስጥ የተደበቀ የበፊቱ ፍፁም እየታያቸዉ
"ዉይ ዉይ አፈር በበላሁ ልጄ ልጄ ልጄ"
ማልቀስ ጀመሩ ለፍፁም ሳይሆን ከሞተች አመታቶች ያለፋት ቤዛዊት ፍፁምን ሲያዩት ፊታቸዉ ላይ ድቅን ብላባቸዉ እንጂ።
ፍፁም የቤዛዊት በህይወት አለመኖር ዉስጡ እየነገረዉ ነበር ወደ ቤት ዉስጥ እያለቀሰ ገብቶ ተቀመጠ ማዉራት አቅቶት በአይኑ ዳግማዊትን አያት
አይኖቿ ላይ ለማታዉቃት ለወለደቻት እናቷ እንባወች ይታዩበታል
ከተቀመጠበት ተነስቶ ተጠጋት
"ዳግማዊት አባትሽ ነኝ"
አቀፋት ወደ ደረቱ አስጠግቶ የብዙ አመት ናፍቆቱን ሀሳቡን በለቅሶ እየተንሰቀሰቀ ልጁን አቅፎ
ማንባት ቀጠለ ቤዛዊት አለመኖሯን የሚያስረሳ ምትክ ስለሰጠችዉ ልጁን ደግሞ ደጋግሞ አቀፋት እስከ ህይወቱ ማብቅያ ለልጁ ለመኖር ቃል እየገባ።

💫ተፈፀመ💫

ስለ ድርሰቱ ያሎትን አስተያየት በ @atronosebot ላይ እንጠብቃለን መልካም ጊዜ
👍3