ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
📢ዓውደ ምህረት🎤

ውድ የዓውደ ምህረት ታዳሚዎቻችን ነገም በወንድማችን #በሙሖዘ ጥበባት በዲያቆን ዳንኤል ክብረት "#መንፈሳዊ አገልግሎት" በሚል ርዕስ እንማማራለን::



የነገ ሰው ይበለን ሰለ ሁሉም የልዑል እግዚአብሔር ስም ከእናቱ #ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል #ማርያም ጋር እና ከወዳጆቹ #ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር የከበረ የተመሰገነ ይሆን ለዘለዓለሙ አሜን❤️


ለማንኛውም ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥቆማ ካለ በ @YeawedMeherte ላይ ያድርሱን::
Audio
የምዕራፍ #አንድ የነገረ #ድኅነት ኮርስ #የመጨረሻ የማጠቃለያ #ክፍል

#በድኅነት ሥራ ውስጥ የእመቤታችን #የቅድስት ድንግል #ማርያም ሱታፌ
#የነገረ_ድኅነት ጥያቄዎች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ሰው ለመዳን ማመኑ ብቻ በቂ ነው::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል #ማርያም በተለየ አካሉ ተወልዶ ያዳነን #እግዚአብሔር አብ ነው::
ሀ) ሐሰት ለ) እውነት

#ኛ ድኅነት አንድ ጊዜ በጌታችን በመድኃታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት በዕለተ አርብ ስለተፈፀመልን እኛ የሰው ልጆች ለመዳን ምንም ጥረተ ማድረግ አይጠበቅብንም

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ኛ የሰው ልጅ የዳነው በመለኮት እና በሥጋ ፍጹም ተዋህዶ ነው::
ሀ) እውነት ለ)ሐሰት

#ኛ የሰው ልጅ በተፈፀመለት የድኀነት ሥራ ያልተመለሰለት ጸጋዎች አሉ::
ሀ) እውነት ለ) ሐሰት


#በአጭሩ መልሱ

#ኛ በቃሉ ብቻ ዳኑ ብሎ ማዳን ሲችል ስለምን ሰው ሆኖ ሊያድነን ወደደ

#ኛ አንድ ሰው ለመዳን የሚያስፈልገውን መሠረታዊ ነገሮች ምን ምን ናቸው በዝርዝር አስረዳ(ጂ)

#ኛ መዳኔዓለም ክርስቶስ የግል አዳኝ ("ዳ"ላልቶ ይነበብ) ሳይሆን የዓለም መድኃን እንደሆነ በቅዱስ ወንጌል ምስክርነት አስረዳ(ጂ)

#ኛ ሰው ጨርሶ ዳነ የሚባለው መቼ ነው

#ኛ "መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ የሐዋሥራ 4÷12 ሲል ምን ለማለት ፈልጎ ነው በትምህርቱ መሠረት አብራራ(ሪ)


#መልሶቻችሁን እስከ ዛሬ ሳምንት ብቻ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#የነገረ_ማርያም ጥያቄዎች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ማርያም ማለት እመ ብዙሐን ማለት ሲሆን በዕብራይስጥ ማሪያም በአርብኛ መሪሃም ተብላ ትጠራለች::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ #ማርያም የሚለው ስም #አብርሃም ከሚለው ስም ጋር ከጾታ ልዮነት ባሻገር በትርጉም ደረጃ አንድ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ኛ የኤልሳ ማሰሮ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሰው ዘር ስለሆነች ጥንተ አብሶ ወይም የመጀመሪያ በደል ነክቷታል::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት

#ኛ_በመዝሙር 86 ላይ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ተብሎ የተነረው ለእመቤታችን ቀደምት አያቶቿ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 44÷ ከቁር 1 እስከ ያለው ኃይለ ቃል ምን ምን ነገሮችን ያስረዳል
ሀ )የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና
ለ)እመቤታችንን የወለደችሁ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የአብን አንድያ ልጅ ወልድ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ::

ሐ) ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ ልጅ ዳግመኛ እንዳልወለደች

መ)ሁሉም

#ኛ_ከእመቤታችን የዘር ሐረግ ውስጥ የማይካተተው ነገድ የቱ ነው

ሀ) ነገደ ሌዊ
ለ) ነገደ ይሁዳ
ሐ) ነገደ ዳን
መ) ሀ ና ለ

#ኛ_ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየው ነቢይ ማን ነው

ሀ) ነብዮ ሳሙኤል
ለ)ነብዮ ኤርምያስ
ሐ)ነብዮ ኢሳይያስ
መ)ነብዮ ሐጌ

፱ እመቤታችን ለዮሴፍ የታጨችበት ምክንያት ምን ነበር

ሀ) ከውግረት እድትድን
ለ) ለጋብቻ
ሐ) ለጠባቂነት እና ለአገልጋይነት
መ) ከ "ለ" በስተቀር ሁሉም መልስ ነው


#ኛ_ እመቤታችን በቤተ መቅደስ የኖረችው ለስንት ዓመታት ነው

ሀ) ፲ ፪ ዓመታት
ለ) ፫ ዓመት ከ፫ ወር
ሐ) ለ፫ ዓመታት
መ)ለ፲ ፭ ዓመታት


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ድኅነት ያበረከተችሁን ትልቅ አስተዋጽኦ አብራራ(ሪ)

፲ ፪ #_ድንግል ማርያም በሦስት መሠረታዊ ነገሮች ንጽዕት ነች ::እነዚህ ሦስቱ መሠረታዊ ንጽዕናዋ የምን የምን ንጽዕና ናቸው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

፲ ፫ #እመቤታችን " እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትሁልድ ሁሉ ብጽህይት ይሉኛል" ሉቃ 1÷49 ብላ የተናገረችሁ ስለምንድነው? ትውልዱ #ሁሉ ያለችውስ የትኛውን ትውልድ ነው

፲ ፬ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በፊት በአምላክ ዕሊና ታስባ ትኖር እንደነበር በትምህርቱ መሠረት ቅዱሳት መጻሕፍትን እያመሳከርክ አስረዳ (ጂ)


፲ ፭ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም #ጺዮን (አንባ መጠጊያ )ተብላ እንደምትጠራ ግልጥ ነው:: ስለሆነም መጻሕፍ ቅዱክ ጺዮን ብሎ ስለ #እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል #ማርያም ከተናከራቸው ንግግሮች መካከል ቢያንስ ፫ቱን ጥቀስ(ሺ)

#መልሶቻችሁን እስከ ዛሬ ሳምንት ብቻ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#የነገረ_ማርያም ጥያቄዎች ምላሾች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ማርያም ማለት እመ ብዙሐን ማለት ሲሆን በዕብራይስጥ ማሪያም በአርብኛ መሪሃም ተብላ ትጠራለች::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ #ማርያም የሚለው ስም #አብርሃም ከሚለው ስም ጋር ከጾታ ልዮነት ባሻገር በትርጉም ደረጃ አንድ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ማርያም ማለት:- እመ ብዙኃን ፣የብዙኃን እናት ማለት ነው

#አብርሃም:- ማለት አበ ብዙኃን፣ የብዙኃን አባት ማለት ነው

#ኛ የኤልሳ ማሰሮ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

የኤልሳ ማሰሮ በውስጧ አጣፋጭ ጨው ተገኝቶባታል ከእመቤታችንም እናንተ የዓለም ጨው ናችሁ ብሎ ማጣፈጥን ለቅዱሳን የሰጠ የአዳምንም ሕይወት በከበረ ሞቱ ያጣፈጠ የአማናዊው #ጨው የክርስቶስ መገኛ ሆናለችና የኤልሳ ማሰሮ #የእመቤታችን ምሳሌዋ ነች

#ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሰው ዘር ስለሆነች ጥንተ አብሶ ወይም የመጀመሪያ በደል ነክቷታል::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት
ምንም እንኳን እመቤታችን የሰው ዘር ብትሆንም በመንፈስ ቅዱስ ልዮ ጠብቆት ከጥንተ አብሶ(ከመጀመሪያው በደል) የነጻች ሆናለች::ወርቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው ::ወርቅ መገኛው ከመሬት ከጭቃ ውስጥ ነው ከጭቃ መገኘቱ ግን ወርቅነቱን አያስቀረውም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከተነከሩ ሰዎች የተገኘች የሰው ፍጡር ብትሆንም ነገር ግን ጭቃው ያላቆሸሻት #ንጹዑ_ወርቅ ነችና ጥንተ አብሶ የለባትም፣ አልነካትም::

#ኛ_በመዝሙር 86 ላይ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ተብሎ የተነረው ለእመቤታችን ቀደምት አያቶቿ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

መጻሕፍትን ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ እንደተባለው ይህንንም ኀሠይለ ቃል አጣመው በወንድ አንቀጽ ቢቀይሩትም እንደ ጥንቱ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ነው የሚለው ::ይህም ሰሸለ እመቤታችን ቅደምት አያቶች ከፍታና ቅድስና የሚናገር አንቀጽ ነው ::


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 44÷ ከቁር 1 እስከ ያለው ኃይለ ቃል ምን ምን ነገሮችን ያስረዳል
ሀ )የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና
ለ)እመቤታችንን የወለደችሁ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የአብን አንድያ ልጅ ወልድ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ::

ሐ) ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ ልጅ ዳግመኛ እንዳልወለደች

መ)ሁሉም

#ኛ_ከእመቤታችን የዘር ሐረግ ውስጥ የማይካተተው ነገድ የቱ ነው

ሀ) ነገደ ሌዊ
ለ) ነገደ ይሁዳ
ሐ) ነገደ ዳን
መ) ሀ ና ለ

#ኛ_ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየው ነቢይ ማን ነው

ሀ) ነብዮ ሳሙኤል
ለ)ነብዮ ኤርምያስ
ሐ)ነብዮ ኢሳይያስ
መ)ነብዮ ሐጌ

፱ እመቤታችን ለዮሴፍ የታጨችበት ምክንያት ምን ነበር

ሀ) ከውግረት እድትድን
ለ) ለጋብቻ
ሐ) ለጠባቂነት እና ለአገልጋይነት
መ) ከ "ለ" በስተቀር ሁሉም መልስ ነው


#ኛ_ እመቤታችን በቤተ መቅደስ የኖረችው ለስንት ዓመታት ነው

ሀ) ፲ ፪ ዓመታት
ለ) ፫ ዓመት ከ፫ ወር
ሐ) ለ፫ ዓመታት
መ)ለ፲ ፭ ዓመታት


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ድኅነት ያበረከተችሁን ትልቅ አስተዋጽኦ አብራራ(ሪ)

#መልስ

#ንጽሕናዋን ጠብቃ በመገኘቷ

#ፍቃዶን ስትጠየቅ እሺ ብላ ለድኅነተ ዓለም ምክንያት በመሆነኗ



፲ ፪ #_ድንግል ማርያም በሦስት መሠረታዊ ነገሮች ንጽዕት ነች ::እነዚህ ሦስቱ መሠረታዊ ንጽዕናዋ የምን የምን ንጽዕና ናቸው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

#በሥጋዋ (ንጽ ሥጋ )
#በነፍሷ (ንጽኃ ነፍስ )
#በሀሳቧ ( ንጽኃ ልቡና )

፲ ፫ #እመቤታችን " እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትሁልድ ሁሉ ብጽህይት ይሉኛል" ሉቃ 1÷49 ብላ የተናገረችሁ ስለምንድነው? ትውልዱ #ሁሉ ያለችውስ የትኛውን ትውልድ ነው

#ይህን የለችሁ
👉ነቢይት ሰለሆነች የወደፊቱን የማወቅ ፀጋ ስላላት እና በተሰጣት ፀጋ እንደ ሰጣት እንደ ፈጣሪዋ አዋቂ ስለሆነች

ትሁልድ ሁሉ ያለችው ደግሞ አማኝ ትውልድ ሁሉ ማለቷ ሲሆን በመጨረሻ ግን ክብሯ ሲገለጥ ሁሉም ትውልድ እንደሚያመሰግናት አውቃ ይህን አለች

፲ ፬ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በፊት በአምላክ ዕሊና ታስባ ትኖር እንደነበር በትምህርቱ መሠረት ቅዱሳት መጻሕፍትን እያመሳከርክ አስረዳ (ጂ)

#መልስ
."እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ እሊና ታስባ ትኖር ነቀር::፡ ለዚህመሸ "ያልተሰራ አካሌን አይኖችህ አዩኝ ፡ የተፈጠሩ ቀኖቸ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመፅሐፍ ተፃፈ" መዝ 138:16
ስለዚህ ዓለም ሳይፈጠር ሁሉም ከተፃፈ እመቤታችንም ተፅፋ ታስባለች ማለት ነው፡፡፡ቅዱሳን ነቢያት(ኤርምያስንና መጥምቁ ዮሐንስን ) ብንመለከት አሰቀድሞ ስለሚያውቃቸው መስክሮላቸዋል፡፡
" በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። " (ኤር1:5)
ስለዚህ የሁሉ አዋቂ ጌታ እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰው መሆኑ ከታወቀና ከታሰበ እመቤታችን መታሰብዋን አይዘነጋም፡፡፡
"፤ #ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4) "፤ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4)

#15.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም "ጽዮን" ተብላ የምትጠራበት የመ/ቅዱስ ጥቅስ፡

"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
(መዝ 87:5)
" የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ፤ የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። "
(ኢሳ60:14)
" ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል እግዚአብሔር። "
(ኢሳ59:20

#በመልሶቹ ዙሪያ ሀሳብ አስተያየት ካላችሁ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
የሀዘን #መግለጫ
😔😔😔😔😔

#ውድ_የቻናሎቻችን ታዳሚዎች በልዮ ልዮ ጊዜ በልዮ ልዮ ምክንያት #በአካለ_ሥጋ_በሞት_ከኛ ከተለዮን #ለምናውቃቸውና_ለማናውቃቸው_ለሁሉም_የሰው_ልጆች _እልፈተ_ሕይወት የተሰማን እና የሚሰማንን #ጥልቅ ሀዘን በእኛና በቻናሎቻችን ተከታዮች ስም ለመግለጽ እንወዳለን::
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
😞😞😞😞😞😞😞😞😞😞😞

"፤ #የሰው_ዕድሜ_የተወሰነ ነው፥ #የወሩም_ቍጥር በአንተ ዘንድ ነው፥ እርሱም ሊተላለፈው የማይችለውን ዳርቻ አደረግህለት።" #ኢዮ 14÷5

😞😞😞😞😞😞😞😞😞😞😞
"፤ #የዘመኖቻችንም ዕድሜ #ሰባ ዓመት፥ ቢበረታም #ሰማንያ ዓመት ነው፤ #ቢበዛ_ግን ድካምና መከራ ነው፤ " #መዝ 88(90)÷10
😞😞😞😞😞😞😞😞😞😞
የሀዘን #መዝሙር
😞😞😞😞😞😞

#ማርያም ሀዘነ ልቡና ታቀልል(2)×
ሀዘነ ልቡና (4)× ታቀልል (2)×

#ማርያም የልብን ሀዘን ታቀላለች(2)×
የልብን ሀዘን(4)× ታቀላለች (2)×

#እግዚአብሔር_አምላክ ነፍሳቸውን #ከአብርሃም_ከይስሐቅ_ከያዕቆብም እቅፍ ያኑርልን #ለዘለዓለሙ_አሜን🙏

ዓውደ ምህረት
@AwediMeherit
የኔታ
@yenetta
መጽሐፈ ጨዋታ
@MtsafiChewata
ስንክሳር ነሐሴ 7
=>+”+ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +”+
+”+ ቁጽረታ (#ጽንሰታ) ለማርያም +”+
=>ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት “ጥንተ መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን” ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ::
“ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ::”
#ድንግል_ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው::” (#መጽሐፈ_ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
+ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::

7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
#ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ #እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው #እናታችን_ጽዮን ይላል:: +”+ (መዝ. 86:1-6) ስንክሳር ነሐሴ 7
=>+”+ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +”+
+”+ ቁጽረታ (#ጽንሰታ) ለማርያም +”+
=>ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት “ጥንተ መድኃኒት_የድኅነት መነሻ ቀን” ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ::
“ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ::”
#ድንግል_ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው::” (#መጽሐፈ_ሰዓታት, ኢሳ. 1:9, መኃ. 4)
+ይሕች ዕለት
ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
=>ነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ "፤ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፤" መዝ 86÷1


"፤ ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል።"
(መዝሙረ ዳዊት 87: 2)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር
>>>
#የነገረ_ድኅነት ጥያቄዎች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ሰው ለመዳን ማመኑ ብቻ በቂ ነው::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል #ማርያም በተለየ አካሉ ተወልዶ ያዳነን #እግዚአብሔር አብ ነው::
ሀ) ሐሰት ለ) እውነት

#ኛ ድኅነት አንድ ጊዜ በጌታችን በመድኃታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት በዕለተ አርብ ስለተፈፀመልን እኛ የሰው ልጆች ለመዳን ምንም ጥረተ ማድረግ አይጠበቅብንም

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ኛ የሰው ልጅ የዳነው በመለኮት እና በሥጋ ፍጹም ተዋህዶ ነው::
ሀ) እውነት ለ)ሐሰት

#ኛ የሰው ልጅ በተፈፀመለት የድኀነት ሥራ ያልተመለሰለት ጸጋዎች አሉ::
ሀ) እውነት ለ) ሐሰት


#በአጭሩ መልሱ

#ኛ በቃሉ ብቻ ዳኑ ብሎ ማዳን ሲችል ስለምን ሰው ሆኖ ሊያድነን ወደደ

#ኛ አንድ ሰው ለመዳን የሚያስፈልገውን መሠረታዊ ነገሮች ምን ምን ናቸው በዝርዝር አስረዳ(ጂ)

#ኛ መዳኃኔዓለም ክርስቶስ የግል አዳኝ ሳይሆን የዓለም መድኃን እንደሆነ በቅዱስ ወንጌል ምስክርነት አስረዳ(ጂ)

#ኛ ሰው ጨርሶ ዳነ የሚባለው መቼ ነው

#ኛ "መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ የሐዋሥራ 4÷12 ሲል ምን ለማለት ፈልጎ ነው አብራሩ።

#መልሶቻችሁን

@Amtcombot

ላይ ይላኩልን ::

🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ሰንበተ_ሰንበታት_ማርያም_ዕለተ_ብርሃን (፪)
#ይወጽኡ ኃጥአን እምደይን (፬)

#ትርጉም
የዕረፍታችን ዕረፍት #ማርያም_የብርሃን ዕለት ነሽ፤ (፪)
ይወጣሉ ኃጥኣን ከጥልቁ (፬)
#ማርያም_ዐርጋለች

ማርያም አርጋለች ወደ ገነት (2) 
የሰማይ መላእክት እያረጋጓትት 
እርሷም እንደ ልጇ ተነሥታለች 


የአባቷ ዳዊትን ትንቢት ልትፈጽም 
ወርቁን ተጎናጽፋ በቀኙ ልትቆም 
ወደ አምላክ ማደሪያ ወደ ሰማያት 
ዐረገች በእልልታ ድንገል የኛ እናት 
ዐርጋለች ማርያም ተነሥታለች 

#አዝ » » » »
 
ሰማይም ይከፈት ደመናም ይዘርጋ 
ዝምታ አይኖርም እመ አምላክ ዐርጋ 
አንደበት ይከፈት ማርያምን ያመስግን 
ከዘለዓለም ጥፋት በምልጃዋ እንድንድን 
አርጋለች ማርያም ተነሥታለች 
#አዝ » » » »
የአምላክ ማደርያ ያ ቅዱስ ሥጋሽ 
አምላክን ያቀፉት እነዚያ እጆችሽ 
ሙስና መቃብር ይዞ አላስቀራቸው 
ተነሥተዋል በክብር በእምነት አየናቸው 
ዐርጋለች ማርያም ተነሥታለች 
#አዝ » » » »
ሐዋርያት አበው እንኳን ደስ ያላችሁ 
በክብር ዐረገች ማርያም ሞገሳችሁ 
ወደ ዓለምም ውጡ ሰበኗን ይዛችሁ 
የድንግል ዕርገቷን ንገሩ ተግታችሁ 
ዐርጋለች ማርያም ተነሥታለች 
#አዝ » » » »

#ሊቀ_መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
አርጋለች #ማርያም ተነስታለች!
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን።

"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ!"

"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ!"
ቅዳሴ ማርያም

ዛሬ ....
#ለክርስቶስ ጸሀይ ምስራቅ ድንግል #ማርያም የተወለደችበት ቀን ነው ።
(አንቲ ምስራቁ ለክርቶስ እንዲል ቅዱስ ህርያቆስ)

#ለክርስቶስ ዝናብ ደመና ድንግል #ማርያም የተዘረጋችበት ነው ።
(አንቲ በአማን ደመና እንተ አስተርያ ለነ ማየ ዝናም እንዲል ቅዱስ ያሬድ በዝማሬው)

#ለክርስቶስ መብል ፍሬ ድንግል #ማርያም የተተከለችበት ነው ።
(እስመ ወለድኪ ለነ መብልዓ ጽድቅ ዘበአማን እንዲል ቅዳሴ ማርያም )

#መልካም_በዓል
#የልደትሽ_ቀን_ልደታችን_ነው
#ስለ_ሀገር_መጸለይን_አታስታጉሉ


©️ ከመምህር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደሳለኝ
#ደስ ይበልሽ#

-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።

-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።

- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።

- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።

"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)

- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።

-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"

-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።

#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!

-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!

#ኢዮብ ክንፈ

#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
#ኖላዊ ወበግዕ#(እረኛም በግም)

#ትጉህ #እረኛችን #አማኑኤል ከድንግል #ማርያም ተወልዶ በበረት ተኛ።ቅዱስ ዳዊት “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”(መዝ 121፥4) ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ በበረት ውስጥ ተኛ።(ሉቃ 2:7)

#እረኛ ሲሆን በግ ፣ በግ ሲሆን እረኛ ነው።መልአኩም በጎቹን (ምዕመናንን) ተግቶ የሚጠብቅ የጌታን ልደት ያበሠረው መንጎቻቸውን ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች ነው።በእረኛነቱ ይጠብቀናል ፤ በበግነቱም በመስቀል ላይ ተሠውቶልናል (ዮሐ 1:29)።

#የጌታችን እረኛነት ግን ልዩ ነው።እረኛ በጎቹን አስብቶ ኋላ ይበላቸዋል ወይም ሽጧቸው ጥቅም ያገኛል።ይህ እረኛችን ግን ስለ ራሱ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
(ዮሐ 10፥11) ሲል ተናግሯል።

#እርሱ ከሚገኝባት የበጎች በረት (ከቤተክርስቲያን) ያልሆኑ ሌሎች በጎችን አስመልክቶ ሩኅሩኅ እረኛ #መድኃኔዓለም እንዲህ ይላል “ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”(ዮሐ 10፥16)

#በዓሉን አከባበራችን ሁሉ የተዘክሮተ #እግዚአብሔር ሊሆን ይገባዋል።ስንበላ እውነተኛ መብላችን ክርስቶስ መወለዱን ፤ ስንጠጣም እውነተኛ መጠጣችን አምላካችን መወለዱን ፤ ስንለብስ ስናጌጥም እውነተኛ ልብሳችን ክርሰቶስ መወለዱን ልናስብ ይገባናል።ይህ ካልሆነ ግን ጌታ ለእኛ ያደረገውን ውለታ የዘነጋን ውለተ ቢሶች እንሆናለን።
በዓሉን በዓል የሚያደርገውም የጌታን የፈቃድ ተዋርዶውንና ውለታውን እያሰብን ካመሰገንን ብቻ ነው ፤ እንጂ የምግብና መጠጡ ጉዳይ አይደለም።ይህን #የጌታችን ውለታ ከሚያረሳሱ የቴሌቪዥን መርኃግብሮችን ሁሉ ልንጠነቀቅም ይገባናል!!!

#በዓለ #ልደቱን በተዘክሮ እግዚአብሔር እንድናከብር አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን!!!

#በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ
#ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ!!!

ልደተ #እግዚእ / 2017 ዓ.ም
#ከሕግ በላይ ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ንጽሕት ነሽ።ከአንቺ በቀር መርገመ አዳም ወሔዋን የቀረለት የለምና።
#ከሕግ በላይ ጌታን በድንግልና ፀንሰሽ በድንግልና ወለድሽ።ድንግልም እናትም ሆንሽ፤ያውም ወላዲተ አምላክ
#ከሕግም ውጪ መርገም ሳያገኝሽ ኃጢአት ሳይኖርብሽ ሞትን ቀመስሽ።ሞት የኃጢአት ውጤት ነውና!!!
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ #ለማርያም የዐፅብ ለኩሉ"
"ሞትስ ለሟች ይገባል ፤ #የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል"

#ኃጢአትን ሳይሠሩ ሞትን መቅመስ(ሞተ ሥጋም ቢሆን በቀደመው በደል የመጣ ነውና) ፤ ደግሞ ኃጢአትን ሠርቶ #በእመቤታችን የዕረፍት ቃልኪዳን ተማምኖ ዝክር አድርጎ ከዳግም ሞት መዳን!!!
#የእግዚአብሔር ፍርዱ ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!

#የእመቤታችን በረከቷ ይደርብን፤ፍቅሯ አይለየን!!!

#አስተርእዮ #ማርያም / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት" የዘወትር ጸሎታችን ነው።አስቀድሞ በማኅፀነ #ድንግል ሥጋችንን ቃል ስለተዋሐደው በባሕርይ አምላክነት (በፈጣሪነት) ዐርጓል (ከፍ ከፍ ብሏል)።ሆኖም ግን እስከ ትንሣኤ ድረስ የትሕትናን ሥራ ከልዕልና ጋር ሲሠራ ቆይቷል።ከትንሣኤ በኋላ እስከ ዐርባ ቀን ድረስ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ለቅዱሳን #ሐዋርያት ሲያስተምር ቆይቶ በአርባኛው ቀን በግርማና በስብሐት ወደ ሰማይ ዐረገ፤በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ።

‎አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።

‎ "ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።

‎ "በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
‎ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።

#ዕርገትን ስናስብ

#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
‎“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
‎“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
‎ በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
‎ "የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!

‎ ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
‎ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም


"ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት" የዘወትር ጸሎታችን ነው።አስቀድሞ በማኅፀነ #ድንግል ሥጋችንን ቃል ስለተዋሐደው በባሕርይ አምላክነት (በፈጣሪነት) ዐርጓል (ከፍ ከፍ ብሏል)።ሆኖም ግን እስከ ትንሣኤ ድረስ የትሕትናን ሥራ ከልዕልና ጋር ሲሠራ ቆይቷል።ከትንሣኤ በኋላ እስከ ዐርባ ቀን ድረስ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ለቅዱሳን #ሐዋርያት ሲያስተምር ቆይቶ በአርባኛው ቀን በግርማና በስብሐት ወደ ሰማይ ዐረገ፤በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ።

‎አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።

‎ "ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።

‎ "በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
‎ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።

#ዕርገትን ስናስብ

#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
‎“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
‎“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
‎ በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
‎ "የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!

‎ ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
‎ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም