ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የነገረ_ማርያም ጥያቄዎች ምላሾች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ማርያም ማለት እመ ብዙሐን ማለት ሲሆን በዕብራይስጥ ማሪያም በአርብኛ መሪሃም ተብላ ትጠራለች::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ #ማርያም የሚለው ስም #አብርሃም ከሚለው ስም ጋር ከጾታ ልዮነት ባሻገር በትርጉም ደረጃ አንድ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ማርያም ማለት:- እመ ብዙኃን ፣የብዙኃን እናት ማለት ነው

#አብርሃም:- ማለት አበ ብዙኃን፣ የብዙኃን አባት ማለት ነው

#ኛ የኤልሳ ማሰሮ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

የኤልሳ ማሰሮ በውስጧ አጣፋጭ ጨው ተገኝቶባታል ከእመቤታችንም እናንተ የዓለም ጨው ናችሁ ብሎ ማጣፈጥን ለቅዱሳን የሰጠ የአዳምንም ሕይወት በከበረ ሞቱ ያጣፈጠ የአማናዊው #ጨው የክርስቶስ መገኛ ሆናለችና የኤልሳ ማሰሮ #የእመቤታችን ምሳሌዋ ነች

#ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሰው ዘር ስለሆነች ጥንተ አብሶ ወይም የመጀመሪያ በደል ነክቷታል::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት
ምንም እንኳን እመቤታችን የሰው ዘር ብትሆንም በመንፈስ ቅዱስ ልዮ ጠብቆት ከጥንተ አብሶ(ከመጀመሪያው በደል) የነጻች ሆናለች::ወርቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው ::ወርቅ መገኛው ከመሬት ከጭቃ ውስጥ ነው ከጭቃ መገኘቱ ግን ወርቅነቱን አያስቀረውም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከተነከሩ ሰዎች የተገኘች የሰው ፍጡር ብትሆንም ነገር ግን ጭቃው ያላቆሸሻት #ንጹዑ_ወርቅ ነችና ጥንተ አብሶ የለባትም፣ አልነካትም::

#ኛ_በመዝሙር 86 ላይ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ተብሎ የተነረው ለእመቤታችን ቀደምት አያቶቿ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

መጻሕፍትን ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ እንደተባለው ይህንንም ኀሠይለ ቃል አጣመው በወንድ አንቀጽ ቢቀይሩትም እንደ ጥንቱ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ነው የሚለው ::ይህም ሰሸለ እመቤታችን ቅደምት አያቶች ከፍታና ቅድስና የሚናገር አንቀጽ ነው ::


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 44÷ ከቁር 1 እስከ ያለው ኃይለ ቃል ምን ምን ነገሮችን ያስረዳል
ሀ )የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና
ለ)እመቤታችንን የወለደችሁ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የአብን አንድያ ልጅ ወልድ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ::

ሐ) ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ ልጅ ዳግመኛ እንዳልወለደች

መ)ሁሉም

#ኛ_ከእመቤታችን የዘር ሐረግ ውስጥ የማይካተተው ነገድ የቱ ነው

ሀ) ነገደ ሌዊ
ለ) ነገደ ይሁዳ
ሐ) ነገደ ዳን
መ) ሀ ና ለ

#ኛ_ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየው ነቢይ ማን ነው

ሀ) ነብዮ ሳሙኤል
ለ)ነብዮ ኤርምያስ
ሐ)ነብዮ ኢሳይያስ
መ)ነብዮ ሐጌ

፱ እመቤታችን ለዮሴፍ የታጨችበት ምክንያት ምን ነበር

ሀ) ከውግረት እድትድን
ለ) ለጋብቻ
ሐ) ለጠባቂነት እና ለአገልጋይነት
መ) ከ "ለ" በስተቀር ሁሉም መልስ ነው


#ኛ_ እመቤታችን በቤተ መቅደስ የኖረችው ለስንት ዓመታት ነው

ሀ) ፲ ፪ ዓመታት
ለ) ፫ ዓመት ከ፫ ወር
ሐ) ለ፫ ዓመታት
መ)ለ፲ ፭ ዓመታት


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ድኅነት ያበረከተችሁን ትልቅ አስተዋጽኦ አብራራ(ሪ)

#መልስ

#ንጽሕናዋን ጠብቃ በመገኘቷ

#ፍቃዶን ስትጠየቅ እሺ ብላ ለድኅነተ ዓለም ምክንያት በመሆነኗ



፲ ፪ #_ድንግል ማርያም በሦስት መሠረታዊ ነገሮች ንጽዕት ነች ::እነዚህ ሦስቱ መሠረታዊ ንጽዕናዋ የምን የምን ንጽዕና ናቸው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

#በሥጋዋ (ንጽ ሥጋ )
#በነፍሷ (ንጽኃ ነፍስ )
#በሀሳቧ ( ንጽኃ ልቡና )

፲ ፫ #እመቤታችን " እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትሁልድ ሁሉ ብጽህይት ይሉኛል" ሉቃ 1÷49 ብላ የተናገረችሁ ስለምንድነው? ትውልዱ #ሁሉ ያለችውስ የትኛውን ትውልድ ነው

#ይህን የለችሁ
👉ነቢይት ሰለሆነች የወደፊቱን የማወቅ ፀጋ ስላላት እና በተሰጣት ፀጋ እንደ ሰጣት እንደ ፈጣሪዋ አዋቂ ስለሆነች

ትሁልድ ሁሉ ያለችው ደግሞ አማኝ ትውልድ ሁሉ ማለቷ ሲሆን በመጨረሻ ግን ክብሯ ሲገለጥ ሁሉም ትውልድ እንደሚያመሰግናት አውቃ ይህን አለች

፲ ፬ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በፊት በአምላክ ዕሊና ታስባ ትኖር እንደነበር በትምህርቱ መሠረት ቅዱሳት መጻሕፍትን እያመሳከርክ አስረዳ (ጂ)

#መልስ
."እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ እሊና ታስባ ትኖር ነቀር::፡ ለዚህመሸ "ያልተሰራ አካሌን አይኖችህ አዩኝ ፡ የተፈጠሩ ቀኖቸ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመፅሐፍ ተፃፈ" መዝ 138:16
ስለዚህ ዓለም ሳይፈጠር ሁሉም ከተፃፈ እመቤታችንም ተፅፋ ታስባለች ማለት ነው፡፡፡ቅዱሳን ነቢያት(ኤርምያስንና መጥምቁ ዮሐንስን ) ብንመለከት አሰቀድሞ ስለሚያውቃቸው መስክሮላቸዋል፡፡
" በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። " (ኤር1:5)
ስለዚህ የሁሉ አዋቂ ጌታ እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰው መሆኑ ከታወቀና ከታሰበ እመቤታችን መታሰብዋን አይዘነጋም፡፡፡
"፤ #ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4) "፤ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4)

#15.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም "ጽዮን" ተብላ የምትጠራበት የመ/ቅዱስ ጥቅስ፡

"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
(መዝ 87:5)
" የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ፤ የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። "
(ኢሳ60:14)
" ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል እግዚአብሔር። "
(ኢሳ59:20

#በመልሶቹ ዙሪያ ሀሳብ አስተያየት ካላችሁ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ይህን ያለው ሻለቃ ኃይለ ገብረ ሥላሴ አይደለም ። እንዲ ያለው የደማስቆው ሯጭ ቅዱስ ጳውሎስ ነው ። “በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።” #1ኛ ቆሮ 9፥24 ክርስቲያኖች የዚህች ዓለም ዙር እስኪያልቅ ድረስ በትጋት እና በውድድር መንፈስ መሮጥ አለባቸው ። ያሸነፉ ሁሉ እንጂ የሮጡ ሁሉ ጥሩ ዋጋን አይሸለሙም። “ እላችኋለሁና ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ 5፥20 በእርግጥ የኑሮ ሩጫ ለየ ቅል ነው እግዚአብሔር ወንዱን ከሴቱ ሕጻኑን ከአዋቂው ደምሮ በአንድ መስፈርት አያወዳድርም ለሁሉም እንደስራው መደብ በጽድቅ ይፈርድለታል እንጂ። ጻድቁ ወደፊት ይጽደቅ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ጠማማውም ወደ ፊት ይጥመም "እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍለው ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ዘንድ አለ እንዳለ ራእይ .ዮሐ22÷12

#ቅዱስ_ጳውሎስ ምርጥ ዕቃዬ ከመባሉ በፊት ሳዉል ይባል ነበር። ሁል ጊዜ ለኦሪት ሕግ የሚቀና ስለነበር ክርስቶስን እንከተላለን የሚሉ ክርስቲያኖች ሲመጡ ከኦሪቷ ሕግ ያፈነገጡ ስለመሰለው እነርሱን ያጠፉ ዘንድ ሌሊትና ቀን ሳይታክት ተሯሩጧል ። #ሐዋ 8፥3

ክርስቲያኖችን ለማሰር ብዙ ጊዜ ሮጧል፤ ክርስቲያኖችን ለማስደብደብ ብዙ ጊዜ ጥሯል፤ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ብዙ ጊዜ ሽምጥ ጋልቧል፤ክርስቲያኖችም በድንጋይ ተወግረው ሲሞቱ የገዳዮችን ልብሶች በደስታ ጠብቆል። ሳውል በዚህ ነገር ሁሉ ሮጧል ግን በምድርም ሆነ በሰማይ ኒሻን የሚሸልመው አልነበረም።

#በመጨረሻ ግን ክርስቲያኖችን ጨርሶ ይፈጅ ዘንድም የፍቃድ ደብዳቤ ሊያጽፍ ወደ ደማስቆ ሽምጥ ጋለበ በአጥፊነት መንፈስም ሮጠ #ሐዋ 9÷15

ወደ ከተማዋ ሲገባ ግን በታላቅ ብርሃን ተመታ ከፈረሱም ወድቆ ከብርሃኑ ጸዳል የተነሳ ዐይኑ ታውሮ ማየት ተሳነው ወዲያውም ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የሚል ቃል ሰማ።

#የማሳድድህ_አንተ ማነህ ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል አለው ሳውልም ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ አለው ወደ ደማስቆም ግባ ሐናንያ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ታገኛለህ እርሱ ይፈውስሃል አለው ።

ሳዉልም ከምድር ተነሳ ዐይኖቹም እንደታወሩ ነበሩ እየመሩም ወደ ከተማዋ አገቡት ለሐናንያም የጠርሴስ ሰው ሳውል ወደ እርሱ እንደሚመጣ በራዕይ ተነገረው ።

#ሐናንያ_ግን ስለ ሳውል ክፋት ብዙ ይሰማ ነበርና እንዴት እፈውሰው ዘንድ ይገባልን አለው ። ጌታም ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው። #ሐዋ 9÷ 13-15

#እግዚአብሔር እንዲህ ነው እያሳደድከውም ይወድሃል እየገደልከው ያኖርሃል እያሰርከው ይፈታሃል እየሸሸህው በፍቅር ይከተልሃል ሰዎች እንደ ሸክም ሲቆጥሩህ ሁሉን ቻይ ትከሻህ ያለው ይሆናል ብሎ ይመሰክርልሃል ሰው ኃጢያተኛ እያለህ እርሱ ግን ምርጤ ይልሃል። #እግዚአብሔር እንዲህ ነው!
ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። #ወዲያውም_እንደ_ቅርፊት_ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ በክፉት መንገድ ሮጦ ያተረፈው እውርነትን ተረዳ አሁን ግን በጽድቁም መንገድ መሮጥን መረጠ።“
#እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ #ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን ” ያለ ዐይን መመልከት፣ መሄድ እንዲሁም መሮጥ አይቻልም።
በሥጋ ለመሮጥ ዓይነ ሥጋ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመሮጥ ዐይነ ልቡና ሊኖረን ይገባል ያለ ዐይን እንኳን መሮጥ በደህንነትና በምቶት መራመድ አይቻልም። ዐይን ለሰውነት ሁሉ ወሳኝ አካል ናት በእርግጥ ዐይን አይሮጥም የሚሮጠው እግር ነው ሆኖም መነሻውን መገስገሻውንና መዳረሻውን ዐይን ካላመለከተችሁ እግር ወስዶ ወስዶ ገደል ይከታል ። “ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” #ማቴ 15፥14
ስለሆነም በእግረ ሥጋ ለመሮጥ ዐይነ ሥጋ በእግረ ልቡና ለመሮጥ ዐይነ ልቡና የግድ ያስፈልገናል። #ታገኙ_ዘንድ_ሩጡ " ብሎ ስለ መንፈሳዊ ሩጫ የመከረን ቅዱስ ጳውሎስ ከሥጋው ዐይንና ከልቦናው ዐይን ላይ ጋርዶት የነበረው ቅርፊት ከወደቀለት በኋላ ነው።
#አሁን የሚያሯሩጠው ሳውል ተብሎ አይጠራም ፤ አሁን የሚያሳድደው ሳውል መባሉ ቀርቷል፤አሁን ደብዳቢ መሆኑ አብቅቷል። አሁን ስለ ስሙ ከቦታ ቦታ የሚሯሯጥ ምርጥ ዕቃ ጳውሎስ ሆኗልና አሁን ስለስሙ ከሀገር ወደ ሀገር የሚንከራተት ስደተኛው ሆኗልና ። 2ቆሮ 11÷23-27
ዋጋ ለማግኘት መሮጥ እንዳናይ የጋረደንን ግርዶሽ ከመጣል ይጀምራል ። ከሳውል ዐይን ቅርፊት መሳይ ነገር ወደቀ ሲል ከአስተሳሰቡና ከልቦናውም ዐይን ጭምር ቅርፊቱ እንደወደቀለት ማስተዋል ያስፈልጋል። ክርስቶስን ወዶ እናቱን ማሳደድ ክርስቶስን ወዶ ክርስቲያኖችን መጥላት ይህ የልቡና ግርዶሽ ፣ ይህ የልቡና ሽፋን፣ ይህ የዕሊና ቅርፊትም ነውና። #እግዚአብሔር እንደ ሳውል ነቅሎ ይጣልላቸው አጥርተው ያዮ ዘንድም የተንሸዋረረ ዐይነ ልቦናቸውን ሐናንያ በመሰሉ የቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ያብራላቸው።

#ሃይማኖት የሌላችሁ ወደ ሃይማኖት ሩጡ
#ሃይማኖት ያላችሁ ወደ ምግባር ገስግሱ
#ምግባር ያላችሁ ወደ ትሩፉት ፍጠኑ ወደ ገነት በር ትደርሳላችሁ ተከፍቶም ታገኙታላችሁ ከየት ናችሁ የሚላችሁም አይኖርም። ያን ጊዜ የደማስቆውን ሯጭ ታኙታላችሁ አብራችሁትም “ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ትላላችሁ ። #2ኛ ጢሞ 4፥7


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፳፮/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
ኢትዮጵያ አ.አ ላላችሁ ሁሉ!

#ይህን_ታዮ_ዘንድ_እወዳለሁ !🙏
#ይህን ጊዜ ታናናሾቹ ተራሮች ቡፍ ቡፍ እያሉ እጆቻቸውን በአቸው ላይ ጭነው ያመለጣቸውን ሳቅ ለማፈን ሲሞክሩ አንጋፈው ተራራ ተፈነጣጣ የምራቅ ቅንጣቶችን እንዳይለቁበት በመስጋት ከቀድሞ ይበልጥ አብልጦ ፊቱን በደመና ጋቢ ተከናነበ ። ሳቃቸው የሚጋባ ሳቅ ቢሆንም ከራሱ ቁጭት አልወጣም ነበርና ሳቃቸው በራስ እንደማሾፍ ቆጠረው

ጠላትን ድል በነሳንበት ሀገር እርስ በእርስ ድል ስንነሳሳ ለከረምን ለኛ ትልቅ ውርደት እንደሆነ ባወቃችሁ ጥርሳችሁን በዘነዘና ትነቀሱት ነበር። ለነገሩ የእሳት ልጅ አመድ ነው እናንተም የዚህ ትውልድ አብራክ አይደላችሁምን? አለና በስላቅ አብሯቸው ሳቅ አለ በልቡ ግን ግን ወይ መፍለስን ወይ መፍረስን ይመኝ ነበር ሰማይና ምድር ያልፋሉ ያለውንም እያሰበ አብዝቶ ያቺን ቀን ናፈቃት ።
_ይኩን ሠላም ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ___
ከኃ/ማርያም ተክለ ኤል
የካቲት 23/2014 ዓ.ም
አ.አ ኢትዮጵያ
#ይህን ያለው ሻለቃ ኃይለ ገብረ ሥላሴ አይደለም ። እንዲ ያለው የደማስቆው ሯጭ ቅዱስ ጳውሎስ ነው ። “በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።” #1ኛ ቆሮ 9፥24 ክርስቲያኖች የዚህች ዓለም ዙር እስኪያልቅ ድረስ በትጋት እና በውድድር መንፈስ መሮጥ አለባቸው ። ያሸነፉ ሁሉ እንጂ የሮጡ ሁሉ ጥሩ ዋጋን አይሸለሙም። “ እላችኋለሁና ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ 5፥20 በእርግጥ የኑሮ ሩጫ ለየ ቅል ነው እግዚአብሔር ወንዱን ከሴቱ ሕጻኑን ከአዋቂው ደምሮ በአንድ መስፈርት አያወዳድርም ለሁሉም እንደስራው መደብ በጽድቅ ይፈርድለታል እንጂ። ጻድቁ ወደፊት ይጽደቅ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ጠማማውም ወደ ፊት ይጥመም "እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍለው ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ዘንድ አለ እንዳለ ራእይ .ዮሐ22÷12

#ቅዱስ_ጳውሎስ ምርጥ ዕቃዬ ከመባሉ በፊት ሳዉል ይባል ነበር። ሁል ጊዜ ለኦሪት ሕግ የሚቀና ስለነበር ክርስቶስን እንከተላለን የሚሉ ክርስቲያኖች ሲመጡ ከኦሪቷ ሕግ ያፈነገጡ ስለመሰለው እነርሱን ያጠፉ ዘንድ ሌሊትና ቀን ሳይታክት ተሯሩጧል ። #ሐዋ 8፥3

ክርስቲያኖችን ለማሰር ብዙ ጊዜ ሮጧል፤ ክርስቲያኖችን ለማስደብደብ ብዙ ጊዜ ጥሯል፤ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ብዙ ጊዜ ሽምጥ ጋልቧል፤ክርስቲያኖችም በድንጋይ ተወግረው ሲሞቱ የገዳዮችን ልብሶች በደስታ ጠብቆል። ሳውል በዚህ ነገር ሁሉ ሮጧል ግን በምድርም ሆነ በሰማይ ኒሻን የሚሸልመው አልነበረም።

#በመጨረሻ ግን ክርስቲያኖችን ጨርሶ ይፈጅ ዘንድም የፍቃድ ደብዳቤ ሊያጽፍ ወደ ደማስቆ ሽምጥ ጋለበ በአጥፊነት መንፈስም ሮጠ #ሐዋ 9÷15

ወደ ከተማዋ ሲገባ ግን በታላቅ ብርሃን ተመታ ከፈረሱም ወድቆ ከብርሃኑ ጸዳል የተነሳ ዐይኑ ታውሮ ማየት ተሳነው ወዲያውም ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የሚል ቃል ሰማ።

#የማሳድድህ_አንተ ማነህ ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል አለው ሳውልም ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ አለው ወደ ደማስቆም ግባ ሐናንያ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ታገኛለህ እርሱ ይፈውስሃል አለው ።

ሳዉልም ከምድር ተነሳ ዐይኖቹም እንደታወሩ ነበሩ እየመሩም ወደ ከተማዋ አገቡት ለሐናንያም የጠርሴስ ሰው ሳውል ወደ እርሱ እንደሚመጣ በራዕይ ተነገረው ።

#ሐናንያ_ግን ስለ ሳውል ክፋት ብዙ ይሰማ ነበርና እንዴት እፈውሰው ዘንድ ይገባልን አለው ። ጌታም ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው። #ሐዋ 9÷ 13-15

#እግዚአብሔር እንዲህ ነው እያሳደድከውም ይወድሃል እየገደልከው ያኖርሃል እያሰርከው ይፈታሃል እየሸሸህው በፍቅር ይከተልሃል ሰዎች እንደ ሸክም ሲቆጥሩህ ሁሉን ቻይ ትከሻህ ያለው ይሆናል ብሎ ይመሰክርልሃል ሰው ኃጢያተኛ እያለህ እርሱ ግን ምርጤ ይልሃል። #እግዚአብሔር እንዲህ ነው!
ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። #ወዲያውም_እንደ_ቅርፊት_ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ በክፉት መንገድ ሮጦ ያተረፈው እውርነትን ተረዳ አሁን ግን በጽድቁም መንገድ መሮጥን መረጠ።“
#እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ #ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን ” ያለ ዐይን መመልከት፣ መሄድ እንዲሁም መሮጥ አይቻልም።
በሥጋ ለመሮጥ ዓይነ ሥጋ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመሮጥ ዐይነ ልቡና ሊኖረን ይገባል ያለ ዐይን እንኳን መሮጥ በደህንነትና በምቶት መራመድ አይቻልም። ዐይን ለሰውነት ሁሉ ወሳኝ አካል ናት በእርግጥ ዐይን አይሮጥም የሚሮጠው እግር ነው ሆኖም መነሻውን መገስገሻውንና መዳረሻውን ዐይን ካላመለከተችሁ እግር ወስዶ ወስዶ ገደል ይከታል ። “ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” #ማቴ 15፥14
ስለሆነም በእግረ ሥጋ ለመሮጥ ዐይነ ሥጋ በእግረ ልቡና ለመሮጥ ዐይነ ልቡና የግድ ያስፈልገናል። #ታገኙ_ዘንድ_ሩጡ " ብሎ ስለ መንፈሳዊ ሩጫ የመከረን ቅዱስ ጳውሎስ ከሥጋው ዐይንና ከልቦናው ዐይን ላይ ጋርዶት የነበረው ቅርፊት ከወደቀለት በኋላ ነው።
#አሁን የሚያሯሩጠው ሳውል ተብሎ አይጠራም ፤ አሁን የሚያሳድደው ሳውል መባሉ ቀርቷል፤አሁን ደብዳቢ መሆኑ አብቅቷል። አሁን ስለ ስሙ ከቦታ ቦታ የሚሯሯጥ ምርጥ ዕቃ ጳውሎስ ሆኗልና አሁን ስለስሙ ከሀገር ወደ ሀገር የሚንከራተት ስደተኛው ሆኗልና ። 2ቆሮ 11÷23-27
ዋጋ ለማግኘት መሮጥ እንዳናይ የጋረደንን ግርዶሽ ከመጣል ይጀምራል ። ከሳውል ዐይን ቅርፊት መሳይ ነገር ወደቀ ሲል ከአስተሳሰቡና ከልቦናውም ዐይን ጭምር ቅርፊቱ እንደወደቀለት ማስተዋል ያስፈልጋል። ክርስቶስን ወዶ እናቱን ማሳደድ ክርስቶስን ወዶ ክርስቲያኖችን መጥላት ይህ የልቡና ግርዶሽ ፣ ይህ የልቡና ሽፋን፣ ይህ የዕሊና ቅርፊትም ነውና። #እግዚአብሔር እንደ ሳውል ነቅሎ ይጣልላቸው አጥርተው ያዮ ዘንድም የተንሸዋረረ ዐይነ ልቦናቸውን ሐናንያ በመሰሉ የቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ያብራላቸው።

#ሃይማኖት የሌላችሁ ወደ ሃይማኖት ሩጡ
#ሃይማኖት ያላችሁ ወደ ምግባር ገስግሱ
#ምግባር ያላችሁ ወደ ትሩፉት ፍጠኑ ወደ ገነት በር ትደርሳላችሁ ተከፍቶም ታገኙታላችሁ ከየት ናችሁ የሚላችሁም አይኖርም። ያን ጊዜ የደማስቆውን ሯጭ ታኙታላችሁ አብራችሁትም “ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ትላላችሁ ። #2ኛ ጢሞ 4፥7


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፳፮/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#የገነት ወግ

ከምጽሐት በኃላ ገነት ውስጥ ነው። ቸርነቱ የበዛ መዐቱ የራቀ እግዚአብሔር አምላክ ከሦስት ወጣቶች ሦስት ነገሮች አግኝቶባቸው ገነት አስገባቸው። መቼም እግዚአብሔር አምላክ መንግሥተ ሰማያትን የምታክል ቦታ በጥርኝ ውኃ የሚሸጥ ሞኝ ነጋዴን ይመስላል። #ማቴ10÷41

#ከወጣቶቹ የተገኘባቸው መልካም ነገርም እነኸህ ነበሩ። በአንዱ እምነት በአንዱ ማስተዋል በአንዱ የዋሕነት ነው። ከዚህ የተረፈ የጠለቀ መንፈሳዊ ትጋት የላቸውም በሳምንት አንድ ቀን እሁድ ግጥሚያና ትሬሊንግ ከሌለባቸው ያስቀድሳሉ ከአጽዋማት ሦስቱን መርጠው እንነገሩ ይጦማሉ በቃ ለገነት ዜግነት ያሳጫቸው ይህው ጥቂቱ ጥረታቸው እእና ብዙሁ የእግዚአብሔር ቸርነት ነው።

#ከገነት በአንዱ ዕለት ታድያ አንደኛው ወጣት እንዲ ይላል " እንተ ገነት ገነት እያልን ስንናፍቃት የነበረችሁ ይችሁ ናትን? እንዴ ጠዋት ቅዳሴ ማታ ውዳሴ እረፍቱ ቆይ መቼ ነው ?
ሌላኛው ወጣት ቀበል አድርጎ ታገስ እስቲ በዚህኮ እረፍቱ ምስጋና ምስጋናው እረፍት ሆኖ ነው የሚኖረው ቢሆንም ግን ጥቂት ማረፋችን አይቀርም ሲል ለማጽናናት ሞከረ
ሦስተኛው ወጣት ግን የሱ ጭንቀት ሌላ እንደሆነ ነገራቸው እንዲህ ሲል እረፍት ብቻውን ምን ያደርጋል? በእረፍት ጊዜያችን ሻምፒዮን ስሊግና ላሊጋን የመሳሰሉት የእግር ኳስ ውድድሮችን መከታተል ካልቻልን

የመጀመሪያው ወጣት ጣልቃ ገብቶ አንተ ደሞ እሱንም ለማየትኮ ቅድሚያ የዕረፍት ጊዜ ሊኖረን ይገባል ማታ ውዳሴ ቀን ቅዳሴ ይህው ከገባን ጀምሮ ስንት ሰንበታት አለፉ በሰንበት እንኳ አናርፍም እኮ አለ ምርር ብሎ

#ለምን ካልሆነ እዚሁ ገነት ውስጥ wi fi እንዲገባ ና ለእያንዳንዳችን እስማርት ስልኮች እንዲታደሉን አናደርግም ከዛ በቃ ላሊጋ በል ሻምፒዮን ስሊግ በል በቃ ሁሉ በእጃችን ሆነ ማለት ነው በተጨማሪም ማኅበራዊ ድኅረ ገጾችን ከፍተን ምድር ካሉ ዘመዶቻችን ጋር ያለ ገደብ እንገናኝ ከናፍቆታቸውም እንገላገላለን አይመስላችሁም? ሲል ሀሳብ አቀረበ

ሁለተኛው ወጣት ድንገት ሳይታሰብ ገብቶ አይመስለንም ሲል አንቧረቀበት ጭራሽ ገነት ውስጥ ዋይ ፋይ ? ጭራሽ ገነት ውስጥ እስማርት ስልክ ? ገነትን ገነት ያሰኙት እኮ የነዚህ ነገር አለመኖር ነው አለዚያማ ከምድር በምን ተሻለ ሆሆሆሆ

#ሦስተኛው ወጣት ፈጠን ብሎ ምን ችግር አለው በምድር ሳለን ትዝ አይላችሁም ካህኑ በስማርት ስልክ ተደግፎ ተንስዑ ሲል ዲያቆኑት ቢሆን እያንዳንዱን የመቅደስ እንቅስቃሴ እየቀረጸ እዛው ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች ላይ ሲለቅ አላያችሁም? ስለዚህ ብዙ ችግር ያለው አይመስለኝም አለ

እናንተ ሰዎች ያ በምድር ነው ሆኖም ትክክል ነው ማለት አይደለም።ምክንያቱም የምድሪቱ ቤተ ክርስቲያን የሰማያዊቱ ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናትና። (camera man) ቀራጭነትና ድቁና ፈሪሳዊነትና ክህነት አብረው አይሄዱም። ግማሽ መላጣ ግማሽ ጎፈሬ ብርሃንና ጽልመት እንዴት አንድ ይሆናሉ? ብንችል ለምድር ሰዎች እንጸልይላቸው እንዴት የነርሱን ስዕተት እዚህ እንደግማለን።

#አንዱ ወጣት የሆነ መላ ብልጭ ያለለት በሚመስል ሆናቴ ፍክት ብሎ ቆይ ከዚህ ሁሉ ጭንቅ ለምን ከገነት አንወጣም ?
ሌላኛው ወጣት ከዛስ ? ሲዖል ጥገኝነት እንጠይቅ?
አንተ ባክህ አቀልድ
በቃ ማለቴ ወደ ቀደመ ኑሯችን ወደ ምድር መልሱን ለምን አንላቸውም ???
ይቻላል እንዴ ? ገነትኮ ካገኙ ማጣት ከገቡ መውጣት የለም ማነው የሚያሶጣን?
ቀላልኮነው ለምን ገነት ውስጥ ያልተፈቀደ ነገር ለምን አናደርግም ከዛ በቃ በራሳቸው ጊዜ ያስወጡናል
አረ ባካችሁ ጓደኞቼ ምን ሆናችዋል? አዳምና ሔዋን በገነት ያልተፈቀደውን አድርገው ከገነት ሲባረሩ የምትገለባበጥ የኪሩቤል ሰይፍም ተመዞባቸው ነበር በኛ ደግሞ ይወድቅብን ይሆናል ማን ያውቃል ።
ማለት ገነት ሰይፍ አለ ? ታድያ ሰይፍ ካለ wifi ቢኖር ምን ችግር አለ? ቢያን አመስግነን ቀድሰን አወድሰን ስንጨርስ ትንሽ እንደበርበት ነበር እኮ ።

#ይህን ሲነጋገሩ ከቀደሙት ደጋግ አባቶች አንዱ በለወሳስ የምስጋና ውዳሴ እያቀረበ ወደ ወደ መንበረ መንግሥት ሲጓዝ አያቸው ከንግግራቸውም ያሉበት ቦታ እንዳልተመቻቸውና መውጣት እንደሚሹ ተረዳ መንገዱንም ገታ አድርጎ ወደ ወጣቶቹ ተጠግቶ ሰላምታ ሰጣቸው።
ከግርማ ሞገሱና ከንግግሩ ለዛ ተደመሙ የተነጋገሩትን አንዲቱንም ቃል ባልሰማን ብለውም ተመኙ። ያ ሰው ግን ያለ ዕውቀት እንደተናገሩ ያውቃልና እያለዛዘበ ጠየቃቸው ልጆች ምን ሆናችኋል የምረዳችሁ ነገር አለ አላቸው እነርሱ ግን ለማስቀየስ ተጠቃቀሱና አይ የለም አሉት በጋራ። መልካም ብሎ ጥሏቸው ጉዞዎን ሊቀጥል ሲል ግን አንደኛው ወጣት ግን አንተ ማነህ? ሲል የገነት ጠባቂ ጥጦስን የጠየቀውን ጥያቄ አቀረበለት አብርሃም ነህን አለው ያም ሰው ዝም አለ እሽ ሙሴ ነህን አለው ያ ሰው አለመለሰለትም በቃ ቅዱስ ጳውሎስ ነህን መሆን አለብህ አለው በጥያቄው ሳይሰለች ነኝም አይደለውምም ሳይለው እርሱ ይቆየኝ

ወጣትነት አስቸጋሪ ነው እኔም ወጣት ሳለው ብዙ ጠባያት እየተፈራረቁ አስቸግረውኝ ነበር ግን በእግዚአብሔር ቸርነት በእናቱ አማላጅነት ሁሉም አልፌያቸው እዚህ ደርሻለው ከፈለጋችሁ ከልምዴ በማካፈል ልረዳችሁ እችላለሁ አላቸው። ካልሆነ ግን በሉ በደህና ዋሉ ብሎ ፊቱን አዙሮ መንገዱን ቀጠለ በእውኑ ግን ጥሏቸው ሊሄድ ልቡ አልወደደም ነበር

#ቢያንስ ከልምዱና ከዕውቀቱ ሊያካፍለን ይችላል በገነት ብዙ ስለቆየ መግቢያ መውጫውንም ሊነግረን ይችላል ለምን ሀሳባችንን አንነግረውም ተባባሉ በለወሳስ ቀስ ብለው። ከዛም አንደኛው ፈጠን ብሎ አባት አባቴ አንዴ ቆይ ብሎ ከኋላ ከተል እያለ ተጣራ አንድ ጊዜ አባቴ ሁለት ደቂቃ ይኖሮታል እባካችሁ ለምስጋና ወደ መንበረ መንግሥት እየሄድኩ ነው ከፈለጋችሁ ግን አብራችሁኝ እየሄዳችሁ የፈለጋችሁትን ልትጠይቁኝ ትችላላችሁ አላቸው። እሺ ይሁን አብረኖት እንሄዳለን ብቻ እርሶ መፍትኤ ብቻ ይስጡን መፍትኤስ ከእግዚአብሔር ነው ግን ምን ገጠማችሁ ?

አንደኛው እጆቹን እያፍተለተለ በእግሮቹም ወደፊት አብሯቸው እየተራመደ ይህውሎት አባ እኛ የገነት ኑሮ ሰልችቶናል ወደ ቀደመ ቦታችን ወደ መሬት መመለስ እስፈልጋለን አለ ሁለቱ ሀሳቡን በመደገፍ በአውንታ ጭንቅላታቸውን አነቃነቁ ያ ባለ ግርማ ሞገስ ሰው ግን ፈገግ አለና ለአህያ ማር አይጥማት አሉ ሲል ተረተባቸው ቀጥሎም እርሷስ ሳያቀምሷት ነው አይጥማትም እያሉ የሚያሟት እናተ ቀምሳችሁ ሳለ እንዴት ሳይጥማችሁ ቀረ ለመሆኑ ገነት ምን ጎደለ?

#አንዱ ቀበል አድርጎ ሻምፒዮ ሲሊግ የለ ፤ ላሊጋ የለ ፤ facebook የለ ፤ instageram የለ ፤ ጠዋት ቅዳሴ ማታ ውዳሴ ይሰለቻልኮ አባ

አይ ልጆቼ ይህ ነው ጭንቀታችሁ ይህን እናንተ ያያችሁትን እኮ ብዙዎች ሊያዮት ወደው ሊያዮት አልቻሉም እስራኤል የሰማይ መና ሰለችን ሥጋ አማረን ቢሉ መና ("ና"ይላላ) ሆነው ቀሩ። የተመኙት ሥጋ ተሰጣቸው ከአፋቸው ከተው እንደቀመሱትም ሁሉም እረግፈው ሞቱ ቦታዋም እስከዛሬ ድረስ የምኞት መቃብር ተብላ እየተጠራች ነው። ምነው ከሕይወት ይልቅ የምኞት መቃብርን ሻታችሁ ከመና ይልቅ መና መሆንን ወደደዳችሁ?
#ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ !
__________________________
#የሀገር የሌማት ትሩፋት #ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን ናት !!!
ያለ እርሷ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለም! ስለዚህ አትጨቁኟት

" የተሰወረ መና ያለብሽ #ንጹዑ_የወርቅ_መሶብ አንቺ ነሽ !
|ሶሪያዊው #ቅዱስ ኤፍሬም