ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የነገረ_ማርያም ጥያቄዎች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ማርያም ማለት እመ ብዙሐን ማለት ሲሆን በዕብራይስጥ ማሪያም በአርብኛ መሪሃም ተብላ ትጠራለች::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ #ማርያም የሚለው ስም #አብርሃም ከሚለው ስም ጋር ከጾታ ልዮነት ባሻገር በትርጉም ደረጃ አንድ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ኛ የኤልሳ ማሰሮ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሰው ዘር ስለሆነች ጥንተ አብሶ ወይም የመጀመሪያ በደል ነክቷታል::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት

#ኛ_በመዝሙር 86 ላይ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ተብሎ የተነረው ለእመቤታችን ቀደምት አያቶቿ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 44÷ ከቁር 1 እስከ ያለው ኃይለ ቃል ምን ምን ነገሮችን ያስረዳል
ሀ )የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና
ለ)እመቤታችንን የወለደችሁ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የአብን አንድያ ልጅ ወልድ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ::

ሐ) ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ ልጅ ዳግመኛ እንዳልወለደች

መ)ሁሉም

#ኛ_ከእመቤታችን የዘር ሐረግ ውስጥ የማይካተተው ነገድ የቱ ነው

ሀ) ነገደ ሌዊ
ለ) ነገደ ይሁዳ
ሐ) ነገደ ዳን
መ) ሀ ና ለ

#ኛ_ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየው ነቢይ ማን ነው

ሀ) ነብዮ ሳሙኤል
ለ)ነብዮ ኤርምያስ
ሐ)ነብዮ ኢሳይያስ
መ)ነብዮ ሐጌ

፱ እመቤታችን ለዮሴፍ የታጨችበት ምክንያት ምን ነበር

ሀ) ከውግረት እድትድን
ለ) ለጋብቻ
ሐ) ለጠባቂነት እና ለአገልጋይነት
መ) ከ "ለ" በስተቀር ሁሉም መልስ ነው


#ኛ_ እመቤታችን በቤተ መቅደስ የኖረችው ለስንት ዓመታት ነው

ሀ) ፲ ፪ ዓመታት
ለ) ፫ ዓመት ከ፫ ወር
ሐ) ለ፫ ዓመታት
መ)ለ፲ ፭ ዓመታት


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ድኅነት ያበረከተችሁን ትልቅ አስተዋጽኦ አብራራ(ሪ)

፲ ፪ #_ድንግል ማርያም በሦስት መሠረታዊ ነገሮች ንጽዕት ነች ::እነዚህ ሦስቱ መሠረታዊ ንጽዕናዋ የምን የምን ንጽዕና ናቸው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

፲ ፫ #እመቤታችን " እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትሁልድ ሁሉ ብጽህይት ይሉኛል" ሉቃ 1÷49 ብላ የተናገረችሁ ስለምንድነው? ትውልዱ #ሁሉ ያለችውስ የትኛውን ትውልድ ነው

፲ ፬ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በፊት በአምላክ ዕሊና ታስባ ትኖር እንደነበር በትምህርቱ መሠረት ቅዱሳት መጻሕፍትን እያመሳከርክ አስረዳ (ጂ)


፲ ፭ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም #ጺዮን (አንባ መጠጊያ )ተብላ እንደምትጠራ ግልጥ ነው:: ስለሆነም መጻሕፍ ቅዱክ ጺዮን ብሎ ስለ #እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል #ማርያም ከተናከራቸው ንግግሮች መካከል ቢያንስ ፫ቱን ጥቀስ(ሺ)

#መልሶቻችሁን እስከ ዛሬ ሳምንት ብቻ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#የነገረ_ማርያም ጥያቄዎች ምላሾች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ማርያም ማለት እመ ብዙሐን ማለት ሲሆን በዕብራይስጥ ማሪያም በአርብኛ መሪሃም ተብላ ትጠራለች::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ #ማርያም የሚለው ስም #አብርሃም ከሚለው ስም ጋር ከጾታ ልዮነት ባሻገር በትርጉም ደረጃ አንድ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ማርያም ማለት:- እመ ብዙኃን ፣የብዙኃን እናት ማለት ነው

#አብርሃም:- ማለት አበ ብዙኃን፣ የብዙኃን አባት ማለት ነው

#ኛ የኤልሳ ማሰሮ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

የኤልሳ ማሰሮ በውስጧ አጣፋጭ ጨው ተገኝቶባታል ከእመቤታችንም እናንተ የዓለም ጨው ናችሁ ብሎ ማጣፈጥን ለቅዱሳን የሰጠ የአዳምንም ሕይወት በከበረ ሞቱ ያጣፈጠ የአማናዊው #ጨው የክርስቶስ መገኛ ሆናለችና የኤልሳ ማሰሮ #የእመቤታችን ምሳሌዋ ነች

#ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሰው ዘር ስለሆነች ጥንተ አብሶ ወይም የመጀመሪያ በደል ነክቷታል::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት
ምንም እንኳን እመቤታችን የሰው ዘር ብትሆንም በመንፈስ ቅዱስ ልዮ ጠብቆት ከጥንተ አብሶ(ከመጀመሪያው በደል) የነጻች ሆናለች::ወርቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው ::ወርቅ መገኛው ከመሬት ከጭቃ ውስጥ ነው ከጭቃ መገኘቱ ግን ወርቅነቱን አያስቀረውም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከተነከሩ ሰዎች የተገኘች የሰው ፍጡር ብትሆንም ነገር ግን ጭቃው ያላቆሸሻት #ንጹዑ_ወርቅ ነችና ጥንተ አብሶ የለባትም፣ አልነካትም::

#ኛ_በመዝሙር 86 ላይ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ተብሎ የተነረው ለእመቤታችን ቀደምት አያቶቿ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

መጻሕፍትን ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ እንደተባለው ይህንንም ኀሠይለ ቃል አጣመው በወንድ አንቀጽ ቢቀይሩትም እንደ ጥንቱ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ነው የሚለው ::ይህም ሰሸለ እመቤታችን ቅደምት አያቶች ከፍታና ቅድስና የሚናገር አንቀጽ ነው ::


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 44÷ ከቁር 1 እስከ ያለው ኃይለ ቃል ምን ምን ነገሮችን ያስረዳል
ሀ )የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና
ለ)እመቤታችንን የወለደችሁ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የአብን አንድያ ልጅ ወልድ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ::

ሐ) ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ ልጅ ዳግመኛ እንዳልወለደች

መ)ሁሉም

#ኛ_ከእመቤታችን የዘር ሐረግ ውስጥ የማይካተተው ነገድ የቱ ነው

ሀ) ነገደ ሌዊ
ለ) ነገደ ይሁዳ
ሐ) ነገደ ዳን
መ) ሀ ና ለ

#ኛ_ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየው ነቢይ ማን ነው

ሀ) ነብዮ ሳሙኤል
ለ)ነብዮ ኤርምያስ
ሐ)ነብዮ ኢሳይያስ
መ)ነብዮ ሐጌ

፱ እመቤታችን ለዮሴፍ የታጨችበት ምክንያት ምን ነበር

ሀ) ከውግረት እድትድን
ለ) ለጋብቻ
ሐ) ለጠባቂነት እና ለአገልጋይነት
መ) ከ "ለ" በስተቀር ሁሉም መልስ ነው


#ኛ_ እመቤታችን በቤተ መቅደስ የኖረችው ለስንት ዓመታት ነው

ሀ) ፲ ፪ ዓመታት
ለ) ፫ ዓመት ከ፫ ወር
ሐ) ለ፫ ዓመታት
መ)ለ፲ ፭ ዓመታት


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ድኅነት ያበረከተችሁን ትልቅ አስተዋጽኦ አብራራ(ሪ)

#መልስ

#ንጽሕናዋን ጠብቃ በመገኘቷ

#ፍቃዶን ስትጠየቅ እሺ ብላ ለድኅነተ ዓለም ምክንያት በመሆነኗ



፲ ፪ #_ድንግል ማርያም በሦስት መሠረታዊ ነገሮች ንጽዕት ነች ::እነዚህ ሦስቱ መሠረታዊ ንጽዕናዋ የምን የምን ንጽዕና ናቸው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

#በሥጋዋ (ንጽ ሥጋ )
#በነፍሷ (ንጽኃ ነፍስ )
#በሀሳቧ ( ንጽኃ ልቡና )

፲ ፫ #እመቤታችን " እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትሁልድ ሁሉ ብጽህይት ይሉኛል" ሉቃ 1÷49 ብላ የተናገረችሁ ስለምንድነው? ትውልዱ #ሁሉ ያለችውስ የትኛውን ትውልድ ነው

#ይህን የለችሁ
👉ነቢይት ሰለሆነች የወደፊቱን የማወቅ ፀጋ ስላላት እና በተሰጣት ፀጋ እንደ ሰጣት እንደ ፈጣሪዋ አዋቂ ስለሆነች

ትሁልድ ሁሉ ያለችው ደግሞ አማኝ ትውልድ ሁሉ ማለቷ ሲሆን በመጨረሻ ግን ክብሯ ሲገለጥ ሁሉም ትውልድ እንደሚያመሰግናት አውቃ ይህን አለች

፲ ፬ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በፊት በአምላክ ዕሊና ታስባ ትኖር እንደነበር በትምህርቱ መሠረት ቅዱሳት መጻሕፍትን እያመሳከርክ አስረዳ (ጂ)

#መልስ
."እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ እሊና ታስባ ትኖር ነቀር::፡ ለዚህመሸ "ያልተሰራ አካሌን አይኖችህ አዩኝ ፡ የተፈጠሩ ቀኖቸ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመፅሐፍ ተፃፈ" መዝ 138:16
ስለዚህ ዓለም ሳይፈጠር ሁሉም ከተፃፈ እመቤታችንም ተፅፋ ታስባለች ማለት ነው፡፡፡ቅዱሳን ነቢያት(ኤርምያስንና መጥምቁ ዮሐንስን ) ብንመለከት አሰቀድሞ ስለሚያውቃቸው መስክሮላቸዋል፡፡
" በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። " (ኤር1:5)
ስለዚህ የሁሉ አዋቂ ጌታ እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰው መሆኑ ከታወቀና ከታሰበ እመቤታችን መታሰብዋን አይዘነጋም፡፡፡
"፤ #ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4) "፤ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4)

#15.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም "ጽዮን" ተብላ የምትጠራበት የመ/ቅዱስ ጥቅስ፡

"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
(መዝ 87:5)
" የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ፤ የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። "
(ኢሳ60:14)
" ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል እግዚአብሔር። "
(ኢሳ59:20

#በመልሶቹ ዙሪያ ሀሳብ አስተያየት ካላችሁ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ስለ ጥያቄዎ ከልብ እናመሰግናለን የሕይወትን ቃል ያሰማልን
#የናሆም መድኃኒት ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሃውልት ፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ ፣የነቢያት ትንቢትና ምሳሌ የሆነች እመቤታችንን የመሰሏትን ነገሮች (ምሳሌዎቿን) መጨረስ አይቻልም ነገር ግን ጥቂቶቹን ከመጠነኛ ማብራሪያ ጋር እነሆ

#የአዳም_ተስፋ_ሔዋን ዘፍ 2፥24
እጸ በለስን ከበሉ በኃላ አዳም አንቺ ነሽ ያሳሳትሽኝ ብሎ ሔዋንን ተጣልቶ አባሯት ነበር መላእከ እግዚአብሔር ተገልጾ ዳግመኛም የምትድነው በእርሷ ነውና ሄደህ ፈልገህ አምጣት ብሎታል ፈልጎም አምጥቷታል። ከዚህ በኃላ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን ተስፋ ሆና እንደምትሰጠው አውቆ አባታችን አዳም ሚስቱ ሔዋንን ሕይወቴ ነሽ ብሎ በአንጻር በምሳሌ ይጠራት ነበር። ስለዚህ ዳግሚት ሔዋን እመቤታችን በቀዳማዊት ሔዋን በአዳም ሚስት ትመሰላለች ምሳሌ ከሚመሰልለት ዋና ነገር እንደሚያንስ ሁሉ ምሳሌዋ ቀዳሚት ሔዋንም(የአዳም ሚስት)ከዳግሚቱ ሔዋን(ከእመቤታችን) በእጅጉ ታንሳለች ።

-ቀዳሚት ሔዋን የዲቢሎስን የሐሰት ቃል ሰማች
- #ዳግሚት_ሔዋን የመላእኩ የእውነት ቃል አደመጠች
-ቀዳሚት ሔዋን የሞት ፍሬ በላች
- #ዳግሚት_ሔዋን ኤፍራታ ግን የሕይወት ፍሬ አፈራች
-ቀዳሚት ሔዋን እንደ ስሞ የሕያዋን እናት መሆን ተሳናት
- #ዳግሚት_ሔዋን የሕያዋን ሁሉ ሕያው እናት መሆን ተቻላት
-ቀዳሚት ሔዋን በአዳም ምክንያት በዘር ጸነሰች
- #ዳግሚት_ሔዋን በመንፈስ ቅድስ ምክንያት ያለ ዘር ጸነሰች
-ቀዳሚት ሔዋን እንደ ተፈጥሮ ድንግልናዋን አጥታ ጸነሰች
- #ዳግሚት_ሔዋን በድንግና ጸነሰ
-ቀዳሚት ሔዋን በሕማምና በምጥ ወለደች
- #ዳግሚት_ሔዋን ያ ሕማምና ያለ ምጥ ወለደች
-ቀዳሚት ሔዋን ታላቅና ታናሽ የሆኑ እርስ በእርስ የሚገዳደሉ ሞችና ገዳይ ልጆችን ወለደች
- #ዳግሚት_ሔዋን ግን ቀዳሚ ተከታይ የሌለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስን ብቻ በድንግልና ወለደች

#የአቤል የዋህት ዘፍ 4÷8
ወንድሙ ቃየን ና ውኃ እንጠጣ ብሎ በድንጋይ ጭኖ የገደለው አቤል እጅግ የዋሕ በመሆኑ ነው ። ይህ የአቤል የዋህነት የእመቤታችን ምሳሌ ናት ። የአቤል ልቡና የዋህት ፣ቅን ፣ደግ እንደሆነች እመቤታችንም እንኳን ለሰው ለተጠማ ጥቁር ውሻ የምትራራ እርርይተ ልቡና ነችና የአቤል የዋህት (ደግነቱ ፣ቅንነቱ) ትባላለች። ለቅኖች ደግሞ ምሥጋና ይገባልና በሰማይ በማሕበረ መላእክት በምድር በደቂቀ አዳም ሁሉ ለዘለዓለሙ ትመሰገናለች።መዝ32(33)፥1

#የጌዲዮን ጸምር መጻ መሳ(6)(7)

#የኤልሳዕ_አዲስ_ማሰሮ 2ነገ 2፥20
የፀነሱ ሴቶች ሲጠጡት የሚያሶርዳቸው ወላድ ወንዶችን በጠጡት ጊዜ የሚያኮላሻቸውን የተመረዘውን ማየ ግብጽ (የግብጽን ውኃ) ኤልሳዕ የፈወሰላቸው ጨው የተጨመረባት አዲስ ማሰሮ በመጠቀም ነበር :: ጨው የጨመረበትን ማሰሮ የተመረዘውን ውኃ ቀድቶ ከጨመረበት በኃላ መልሶ ወደ ወንዙ ቢያፈሰው ወንዙ እንደ ቀድሞ ደህነኛ ውኃ ሆነ አዲሷ ማሰሮ የእመቤታችን በውጧ የጨመረው ጨው የልጇ የክርስቶስ ምሳሌ ነው :: ስለዚህ እመቤታችን አልጫው ዓለም የጣፈጠባት፤ የመጣፈጣችን ምክንያት የሆነች ጨው ክርስቶስ የተገኘባት አዲስ ማሰሮ ነች ::


#የሙሴ ጽላት ዘጸአት 24፥12
ታቦት ማደሪያ ሲሆን ጽላት ደግሞ ሰሌዳ መጻፊያ የፊደሉ ቅርጽ ማረፊያ ወይም ያረወበት ማለት ነው ። እመቤታችን ታዲያ የአምላክ ማደሪያ ማህደረ መለኮት በመሆኗ ታቦት የፊደል ክርቶስ መቀረጫ ጽሌ በመሆኗ ደግሞ ጽላት እየተባለች በሁለቱም በማስተባበር ትጠራበታለች ። በጽላት አስርቱ ትዕዛዛቶ እንደተቀረጸ በእመቤታችንም የሕይወት ፊደል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀርጾባታልና ይልቁኑ እርሷ በንጽሕና የተጻፈች ፊደል ናት ማ ር ያ ም!

#ሙሴ ያያት የሲና ዕፀ ጳጦስ ዘጽ3፥2
አመልማል ከነበልባል ነበልባልም ከአመልማል ተዋሕደው በአንድነት ሆነው ሙሴ በደብረ ሲና ተመልከቶ ነበር የሚገርመው አመልማሉ ዘነበልባሉ አይቃጠልም ነበር ነበልባሉም በአመልማሉ አይጠፋም ነበር :: ምነው እንዴት ቢሉ ምሥጢረ ተዋሕዶ ነውና አመልማል የሥጋ ፤ነበልባል ደግሞ የመለኮት አምሳል ነው :: ነበልባሉ አመልማሉን እንዳላቃጠለው ነበልባል የሚባል መለኮትም በድንግል ማርያም ማህፀን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሶም ነፍስ ነስቶ 9ወር ከ5 ቀን ሲቆይ ድንግል ማርያምን አላቃጠላትም ስለዚህ ሙሴ ነበልባል ታቅፋ ያያት አመልማል የእመቤታችን ምሳሌ ናት:: (ማርያም ተአቢይ እምኩሉ ፍጥረት ሕያዋያ አሳተ መለኮት) ማርያም ትበልጣለች ከሁሉም ፍጥረት ስለ ያዘች እሳተ መለኮት እያልንም እንዘምርላት ዘንድ ተገባት።

#የአብርሃም_ድንኳን ዘፍ 13÷1-18
በአብርሃም ድንኳን ቅድስት ሥላሴ ተስተናግደዋል በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ሥላሴ በጉልዕ ተገልጠዋል :: ከእመቤታችን መገኘት በፊት የሥላሴ ምሥጢር በጎላ በተረዳ ነገር አይታወቅም ነበር የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በፍጥረቱ ዘንድ በእጅጉ የጎላውና የተረዳው በድንግል ማርያም ምክንያት ነው:: እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የአብ ማረፊያ የሆነ ማነው ? እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የወልድ ማደሪያ የሆነ ማነው ? እንደ እመቤታችን እንደ ማርያም የመንፈስ ቅዱስ ንጽሕ አዳራሽ የሆነስ ማነው? /እንዲል ተአምረ ማርያም መቅድም/

#በጉ_የተያዘበት_ዕፀ_ሳቤቅ ዘፍ 22፥13
አብርሃም የእምነቱ ጽናት እንዲገለጥ አንድ ልጅህን ሰዋልኝ የሚል ጥያቄ ከእግዚአብሔር ቀረበለት በእስተ እርጅናዬ ያገነውት የምወደው አንድ ልጄን አልሰዋልህም ሳይል የምትነሳኝ ከሆነ ለምን ሰጠህኝ ብሎም ሳያማርር እሺ በጄ ብሎ ልጁ ይስሐቅን የመሰዋይቱን እንጨት አሸክሞ እራሱ ደግሞ ቢላዋን ይዞ ወደ ሞሪያም ተራራ ወጣ ይስሐቅም አባቴ የመሰዋቱን እንጨት እኔ ይዣለሁ መሰዊያውንም ቢላዋ አንተ ይዘሃል መሰዋይቱ ግን አይታየኝም የታለ? አለው አብርሃምም እርሱን #እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው የልጁ የይስሐቅ አሳዛኝ የልጅነት ንግግር ሳያባባው ምሰዋይት አድርጎ ያቀርበው ዘንድ ቆረጠ ለእግዚአብሔር በፍጹም ታምኟልና ከፍቅረ ልጅ ይልቅ ፍቅረ እግዚአብሔር አገብሮታልና። በደረሱ ጊዜም ልጄ ይስሐቅ ሆይ መሰዋይቱ አንተ ነህ እግዚአብሔር አንተን እሰዋለት ዘንድ ወዷል አለው ይስሐቅም አንተ ጨካኝ አባት ሳይል በእሺታ በመሰዊያው ላይ ወጣ አባቴ ዐይን ዐይኔን እያየህ ስቁለጨለጭብህ አዝነህ ትተወኝና ከፈጣሪ እንዳትጣላ በጀርባዬ ገልብጠህ ሰዋኝ አለው እዳለውም አድርጎ ሊሰዋው ሲዘጋጅ አብርሃም አብርሃም በልጅህ ላይ አዳች እንዳታደርግ ተባለ ዞር ሲልም ቀንዶቹ በእጸ ሳቤቅ የተያዘ በግ አየና በይስሐቅ ፈንታ እርሱን መሰዋት አቀረበ:: በዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት የአብርሃም እምነት የይስሐቅም ፍጽም ታዛዢነት ተገለጠ።
#አብርሃም የእግዚአብሔር አብ
#ይስሐቅ የአዳም
#በጉ የእግዚአብሔር ወልድ(የኢየሱስ ክርስቶስ )
#በጎን በቀንዱ በኩል አስራ የያዘችሁ እፀ ሳቤቅ የእመቤታችን ምሳሌ ናቸው።

ሥልጣን ኃይል ብርታት በመጻሕፍ ቅዱስ አገላለጽ " ቀንድ " ተብሎ ይገለጻል ። “ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።” 1ኛ ሳሙኤል 2፥1
“ቀንዴ አንድ ቀንድ እንዳለው ከፍ ከፍ ይላል፤ ሽምግልናዬም በዘይት ይለመልማል።” መዝ 92፥10

ቀንድ በከብቶች ሕይወት ውስጥ ሰፊ ሚና አለው ከብቶች የቀንድ ከብት እና የጋማ ከብት ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ ታዲያ የቀንድ ከብቶች እራሳቸውን ከጥቃት
"ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሣራ ተመልከቱ።" (ኢሳ 51:2)

    ነቢዩ ይህንን ቃል ቅዱስ አብርሃምንና ቅድስት ሣራን ምሰሏቸው ለማለት ተናግሮታል።

#አብርሃም አበ መናንያን (የመናንያን አባት) ነው።ሁሉን ትቶ እግዚአብሔርን ተከትሎአልና።(ዘፍ 12:1)

#አብርሃም የሙሽሮችም አባት ነው።ሚስቱ ምን መካን ብትሆን አልተዋትምና።

#አብርሃም ለሰብዓ ዓለም (በዓለም ለሚኖሩ ክርስቲያኖች) አባት ነው።በሕገ ልቡና ሁኖ ወንጌልን ፈጽሟልና።አረ ግሩም ነው !!! የእግዚአብሔር እንግዳ ቤቴ ሳይመጣ ግብር አላገባም፤እህል አልቀምስም ማለት እንዴት ያለ ብፅዕና ነው!? ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅረ ቢጽ እንዴት ቢጸኑለት ነው!?ደጉ አባታችን የእግዚአብሔር ሰው አብርሃም  ወንጌልን ሲፈጽማት ተመልከቱልኝማ!!!

#"በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና"(ማቴ 5:3) ትሑቱ አብርሃም ባለጠጋ ሆኖ ሳለ ለእኔ የሚስማማ ደህነትነው፤ባለጠግነትማ የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው በማለት መንፈሱን ዝቅ አድርጎ ራሱን እንዳሳላፊ ቆጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ለሌሎች ያካፍል ነበር።በዚህም መንግሥተ ሰማያት (የሰማያት መንግሥት) የሆኑ ሥላሴን አስተናግዷል።መንግሥተ ሰማያት የሚባል ጌታም ከእርሱ ዘር ተወልዷል።"የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።"ማቴ 1:1እንዲል

#“የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።”
(ማቴ 5:4) ርኅሩኁ አብርሃም ለሦስት ቀናት ያህል ሰው ቤቱ ስላልመጣ እጅጉን አዝኗል።ሥላሴን በማግኘት ተጽናንቷል።

#"ስለ  ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።"(ማቴ 5:6) መፍቀሬ ሰብእ ደጉ አብርሃም ስለ ሰው ፍቅር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ተርቧል።ጽድቅ የሚባል እግዚአብሔርን በድንኳኑ ተቀብሎም ጠግቧል (ነፍሱ ተደስታለች) ።

#"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።"(ማቴ 5:10) የሃይማኖት ሰው አብርሃም እግዚአብሔር "ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"(ዘፍ 12:1) ሲለው በፍጹም እምነት ወጥቷል።መንግሥቱንም ወርሷል።

    "አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፤አየም ደስም አለው።" ዮሐ8:56 ማለት እንግዲህ  ይህ ነው።በጨለማው ዘመን ሆኖ ብርሃንን ማየት ወንጌልን መኖር!!!ቅድስት ሥላሴን በቤቱ ተቀብሎ"የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተእመለሳለሁ፤ሣራምልጅንታገኛለች።"ዘፍ18፤14 ባለው ቃል መሠረት ለጊዜው ይስሐቅን እንደሚወልድ ለፍጻሜው ክርስቶስ ከእርሱ እንደሚወለድ ኪዳንን ተቀብሏል።

#በሕገ ልቡና ሕገ ኦሪት በሕገ ኦሪት ሕገ ወንጌል በተሰጠን በእኛ ቅዱስ አብርሃም ይፈርዳል፤ከአብርሃም የሚከብር ጌታ በሥጋ አብርሃም ተወልዶ በጥምቀት ልጅነትን፣በልጅነት መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶን የአብርሃምን ሥራ አልሠራንምና።

        የአብርሃሙ ሥላሴ በሁላችን ቤት ይደሩ!!!

                       ሐምሌ ሥላሴ/2016 ዓ.ም
    #ኢዮብ ክንፈ