ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የቅዱስ_ገብርኤል ጸሎትና ምኞት !
___________________________
ጸሎት ና ምኞት እንዲሁም ተስፋ ማድረግ የሰው ልጆች ብቻ ጠባይ አይደለም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ያለ የፍጡር ሁሉ ጠባይ ጭምር ነው። ታድያ ጸሎት፣ምኞት፣ተስፋን መልካም ካልሆነ ውጤቱም መልካም አይሆንም ለምሳሌ ለእግዚአብሔር የቀረበ ቅሩበ #እግዚአብሔር የሚባል የነበረ ሳጥናኤል ከዚያ ሁሉ ክብሩ የተሻረው ባልተገባ ፈጣሪ የመሆን ምኞትና ተስፋ ነው።

ቅዱሳን መላእክት 24 ሰዓት ያለ ማቆረጥ ያለ መሰልቸት እረፍታቸው ምስጋናቸው ምስጋናቸው እረፍታቸው ሆኖላቸው ሥሉስ ቅዱስ እያሉ ያመሰግናሉ ይዘምራሉ። በምስጋናና በመዝሙር ውስጥ ደግሞ ጸሎትና ልመና አለ። የሰው ልጆችን ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር እንደሚያደርሱ ሁሉ ማር ይቅር በል እያሉ የራሳቸውንም ጸሎትና ልመና ያቀርባሉ ለዚህም ነው ቅዱሳን መላእክት ያማልዱናል የምንለው።ዛሬ ግን ልዮ ጸሎትና ልመና ወደለመነው ወደ ቅዱስ ገብርኤል ምኞትና ጸሎት እናምራ።
#እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለማብሰር የተመረጠው መላእክ ቅዱስ ገብርኤል ነው። ቢሆን ግን ይህን ዕድል ዝም ብሎ አላገኘውም ዕድል ፈንታ ጽዋ ተርታ ዝም ተብሎ የሚገኝ ነገር አይደለምና :: ይህን ዕድል ያገኘውን ቅዱስ ገብርኤልን አነሳን እንጂ ድንግል ማርያም ማብሰር የማኅበረ መላክት ሁሉ ምኞትና ጸሎት ነበር ማለት ይቻላል።
#እመቤታችንን ትጸንሲ ብሎ ለማብሰር መላእክ በሙሉ እኔ ብሆን እያሉ በእጅጉ ይመኑ፣ ይጓጉ ነበር :: ለምን ቢሉ ድንግል ፊት ቆሞ የሰማይና የምድር የሰውና የመላእክት የነፍስና የሥጋ መታረቂያ የጠቡ ግድግዳ መፍረሻ የሥግው ቃል የኢየሱስ ክርስቶስ ማደሪያ የሆንሽ አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ አዳም ከነ ልጆቹ ነፃ የሚወጣበት ጊዜው ደረሰ አንባው ፈረሰ ብሎ ከማብሰር የበለጠ ሌላ የምሥራች በዓለም ላይ የለምና ነው ፡፡
#ቅዱስ_ገብርኤል የዚህ ምሥራች ነጋሪ ሆኖ የተመረጠው አስቀድሞ በዓለመ መላእክ በተፈጠረው የነገደ መላእክት መለያየትን በማረጋጋቱ ነው ፡፡ መላዕክት በተፈጠሩበት በዕለተ እሁድ ቅድሥት ሥላሴ በፈጠርኩላቸው አህምሮ ተጠቅመው አምላክነቴን መርምረው ይወቁ ሲል በዚያው በተፈጠሩበት ቀን ከመንበሩ ተሰወራቸው መላእክትም ከዙፋኑ ቀና ብለው ሲያ አጡት እርስ በእርሳቸውም "መኑ ፈጠረነ?"የፈጠረን ማነው? ሲሉ ተጠያየቁ ሳጥናኤል በክብር ይበልጣቸው ነበርና ቀና ቡሎ ቢመለከት ሥላሴን ከመንበር አጣ ዝቅ ብሎም ቢያይ መላእክ እርስ በእርስ ሲጠያየቁ ተመለከተ ሐሰት የሐሰትም አባቷ እርሱ ነውና "አነ ፈጠረክሙ" እኔ ፈጠርኳችሁ አላቸው ::
ገሚሱ አዎ የበላያችን ስለሆንክ ፈጠርከን ሲሉ ተገዙለት የቀሩት እርሱ ይሆን እያሉ ተጠራጠሩ በዚህ ጊዜ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል ተነስቶ ሳጥናኤል የበላያችን በመሆኑ ወይም በሥልጣን ሰለበለጠን የፈጠረን ከሆነ እኛም የበታቹቻችንን ፈጠርን እንደ ማለት ነው ፈጣሪስ ከሆነ አሁንም ደግሞ ፈጥሮ ያሳየን አለ ሳጥናኤልም እፈጥር ብሎ እጁን ወደ እሳት ቢከት ተቃጥሏል ገብርኤልም እርሱ ፈጣሪ አለመሆኑን ካሳወቀ በኋላ " እንቁም በዕበ ሕላዊከ " የፈጠረንን እስከምናውቅ ባለንበት (በቀደመ እምነታችን) ጸንተን እንቁም ብሎ አረጋጋቸው ::
ከዚህ በኋላ ሥላሴ እራሱን ገለጠላቸው ለሳጥናኤል የተገዙትና የተጠራጠሩትም ከማህበረ ከመላክት ተለይተው ወደ ምድር ተጣሉ በቅዱስ ሳጥናኤል ፈንታ ቅዱስ ሚካኤል ተሾመ መቶ ነገደ መላእክትም ዘጠና ዘጠኝ ነገድ ሆነ በኃላም የሰው ልጅ ተተክቶበተ ነገዱ እንደ ቀድሞ መቶ መሆን ችሏል ::
ቅዱስ ገብርኤልም በዚህ ትልቅ የዕቅበተ እምነት ሥራውና በማረጋጋቱ ቅዱስት ድንግል ማርያምን ለማብሰር ተመረጠ ዕድለኛ መላእክ መሆን ቻለ። ከአዳም ውድቀት በኋላም 5500.ዘመን ሲፈጸም እንደ ተስፈው ቃል ዕድለኛው ቅዱስ ገብርኤል ድንግልን ለማብሰር ሊላክ ከሌሎቱ መላእክት ተለይቶ ወደ አምላኩ ተጠራ ናዝሪት ገሊላ ወደ ምትባለው ቦታ ሂድ ዮሴፍ ለተባለ ሰው የታጨች ድንግልም ታገኛለህ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነው።
ከሷ ደርሰህ የምሥራቹን ነገር ንገራት ስትነግራት ግን ቃልህን ባትቀበልህ በቀስታ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር እንደሌለ አስረዳት እንጂ እንደ ካህኑ ዘካሪያስ እንዳታሳዝናት አለው መላእኩም ክንፉን እያማታ ወደ ገሊላ መንደር ወረደ የክንፉም ድምጽ በገሊላ አውራጃ ሁሉ ይሰማ ነበር:: እመቤታችንም ከእስራኤል ሴቶች ጋር ውኃ ልትቀዳ ወደ ወንዝ ወርዳ ነበር ስተመለስም መላዕኩ እየተከተለ "ትፀንሲ"ትንሻለሽ "ይላት ጀመር
#እመቤታችንም አግብቶ ጸንሶ የመውለድ ሀሳቡ እንኳን አልነበራትምና ይህስ የቀደሙ እናትና አባቶቼን አዳምና ሔዋንን ያሳተ ከይሲ ሳይሆን አይቀርም አለች ወደ ቤተ ዮሴፍም ሄዳ የቀዳችሁን ውኃ ከጀርባዋ ስታወርድ በድጋሚ መላእኩ "ትጸንሲ" (ትጸንሻለሽ) አላት ይህ ነገር ተደጋገመሳ እንዲ ያለውን ነገር እውነት ከሆነ በቤተ መቅደስ መቶ ይነግረኛል ካሎነ ይቀራል ብላ ከእስራኤል ሴቶች የተካፈለችሁን ሐርና ወርቅ ይዛ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደች::
ቤተ መቅደስም ሆና ሐርና ወርቁ እያስማማች ስተፈት ለሦስተኛ ጊዜ መላእኩ ተገልጾ ደስ በሚያሰኝ ንግግር እያረጋጋ ትጸንሲ (ትጸንሻላሽ )አላት እመቤታችንም ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው " ምድር ያለ ዘር ሴት ያለ ወንድ እንዴት ሊያፈሩ ይቻላቸዋል "ይህ ነገር አይሆንም አለችሁ መላእኩም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ የመውለጃዋ ወራት ካለፈ በኃላ ፣ሙቀት ልምላሜ ከተለያት በኃላ ለመውለድ ጸንሳለች ከጸነሰችም ስድስት ወር አልፎታል አላት።
ኤልሳቤጥስ ብትጸንስ ምክንያት ሚሆን ዘካሪያስ አላት እኔ ማን አለኝ አለችሁ መላእኩም ኤልሳቤጥን የመውለጃዋ ጊዜ ካለፈ በኋላ እንድ ትጸንስ ያደረገ አምላክ አንችንም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንሽ ማድረግ ይቻለዋል #ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ::
#እመቤታችንም እውነተኛ መላእክ መሆኑን መርምራ ከተረዳች በኋላ እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ ስትል ምሥራቹን በደስታ ተቀበለች ከዚህች ሰዓት ጀምሮ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ በማህፀኟ ተቀረፀ:: መላእኩም የዚህ ድንቅ ምሥራች አብሳሪ በመሆኑ እየተደሰተ ወደ መጣበት ተመለሰ:: #ሉቃ 1÷26-

..........ይቆየን........
እግዚአብሔር አምላክ ከእመቤታችን እና እርሷን ለማብሰር ከተመረጠው ከዕድለኛው መላእክ ረድኤትና በረከት ይክፈለን !

ተክለ ኤል ኃ/ ማርያም
ታህሳስ ፳ ፪ ቀን ፳ ፻ ፲ ፪ ዓ.ም
ዕድለኛው መላእክ በሚል ርዕስ
ተለጥፎ የነበረ
ባለማወቅ ማወቅ !
" #አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም .... "

ደመና ከማረግ ከማይጋርደው ከእናቶቻችን ጸሎቶች መካከል አልፎ አልፎ የምንሰማው ንግግር ነው። አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም ፣ አንተ የፈጠርከኝ ሚካኤል ....ወ.ዘ.ተ
ታድያ ይህን የየዋሃን ጸሎት የሰማ እንደኔ ያለ በማወቅ ያላወቀ ሰው "እናቴ የፈጠረሽኮ እግዚአብሔር ነው ለምን እንደሱ ትጸልያለሽ ? " ብሎ ለማረም ይቃጣዋል።

በርግጥም ሥነ ፍጥረትን ካለመኖር ወደ መኖር ካለመታየት ወደ መታየት አምጥቶ የፈጠረው ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር ብቻ ነው። ሆኖም ግን ይህ የእናቶቻችን የዋህትን ገንዘብ ያደረገች ንግግራቸው በኃያሌው ትክክል ነች ! እንዴት የሚል ካለ ጥቂት ያንብብ ።

#እናቶቻችን የመረዳት እምነት ሲኖራቸው እኛ ደግሞ የማወቅ እምነት አለን ። እውቀት ተኮር እምነት ለሰዋሰው ፣ ለንግግር ጠባይ ፣ ለነጠላና ብዙ ቁጥር እንዲሁም መደብን ጠብቆ አሳክቶ መናገር ወይም መጻፍ ሲሆን ይህን ያላሞላ ንግግርና ጽሁፍም ስሕተት እንደሆነ እናስባለን ስለዚህ የእናቶቻችን ንግግሮችና ጸሎቶች የሚሰምር አይመስለንም። የመረዳት እምነት ያላቸው እናቶቻችንና አባቶቻችን ግን ትክክለኛውን የእምነት መሠረት በልባቸው ይዘው እና አውቀው ማለትም #እግዚአብሔርን ፈጣሪ #እመቤታችንን እመ ፈጣሪ /የፈጣሪ እናት/ እንደሆኑና እንደሚባሉ እያወቁ ለቋንቋ አጠቃቀማቸው ሳይጨነቁ እርሱ የማያውቀው የለም በማለት በየዋህነት ብቻ አንዱን በአንዱ ሊጣሩበት ይችላሉ።
ለምሳሌ እግዚአብሔር ጠባቂያችን ነው ። ቅዱሳን መላእክትም ጠባቂዎቻችን ናቸው። ታድያ አንድ ሰው ተነስቶ ጠባቂዎቼ ቅዱሳን መላእክ ሆይ ብሎ ቢጸልዬ መላእክቱን ፈጣሪ አደረጋቸው አያሰኝም ።ከፈጣሪ ጋር የሚያመሳስላቸውን አንድ ዘርፍ መርጦ ለጸሎት ተጠቀማቸው እንጂ ፈጣሪና ፍጡርን አስተካለ እኩል አደረገም አያሰኝም። በተመሳሳይ እናቶቻችንም የፈጠርሽኝ እመቤቴ ሲሉ እንደ ፈጣሪ የሆንሽ ፈጣሪን የምትመስይ ማለታቸው ነው። የእመቤታችን የማርያም መልክ የአምላክን መልክ ይመስላል እንደሚል /ተአምረ ማርያም መቅድም / አያይዞም ዓለሙ ሁሉ የተፈጠረው ስለ ድንግል ማርያም እንደሆነ ሲያስረዳ አዳምና ሔዋንም እመቤታችን ከነርሱ (ዘር) እንድትወለድ ተፈጠሩ ይላል።
#ሌላው አዳሪ በማኅደሩ ማኅደርም በአዳሪው ይጠራል። ለምሳሌ ሰይፍ በሰገባው ያድራል ይህን የሚያውቅ ሰው ሰይፉ የተለየው ሰገባን ቢያይና ሰይፉ በሰገባው እንደሌለ ባያስተውል ሰገባውን ሰይፍ ብሎ በአዳሪው ሊጠራው ይችላል ።በተመሳሳይ ዳዊት የሌለው ማኅደር ያየ አንድ ሰውም ማኅደሩን አይቶ ብቻ ዳዊቱን አቀብለኝ ብሎ ማኅደሩን ዳዊት ብሎ ሊጠራው ይችላል ትክክል ነው አዳሪ በማኅደሩ ማኅደሩም በአዳሪው መጥራት ልማድ ነውና ሰውየውን ከመግባባት አያግደውም ።
እናቶቻችንም እመቤታችንን አንቺ የፈጠርሽኝ ማርያም ሲሉ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣሽን ፈጥረሽ የምትመግቢን በኃላም እንደ ብራና ጠቅልለሽ ዓለምን የምታሳልፊ ፈጣሪያችን ነሽ ማለታቸው አይደለም 9ወር ከ5ቀን በማኅጸንሽ ያደረብሽ (የተዋሕደሽ ) ሦስት ዓመት በጀርባሽ ያዘልሽው ሁለት ዓመት ከድንግልና የተገኘ አሊበ ወተት ያጠባሽው እመ ፈጣሪ የፈጣሪ እናት ነሽ፤ እንደ ፈጣሪ የሆነሽ ማለታቸው ነው።
#በርሷ ባደረ በፈጣሪ ልጇ እርሷን ፈጣሪተ ዓለም /የመፈጠር ምክንያት/ ብሎ እንደ መጥራት ነው። ልክ ሰገባውን ሰይፍ ማኅደሩንም ዳዊት ብሎ እንደመጥራት ያለ አጠራር። አንድም በቀደመች ሔዋን እናታችን አማካኝነት ሞት ወደ ዓለም መጣ በዳግሚት ሔዋን በእመቤታችን አማካኝነት ደግሞ በዳግም ተፈጥሮ ሕይወት ተሰጠን ።
ስለሆነም እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የመዳን ምክንያት ብቻ ሳትሆን አዳምና ሔዋንም (የሰው ልጅ ሁሉ) ድንግል ማርያምን ለማመስገን የተፈጠሩ በመሆናቸው የመፈጠራችን ምክንያት ናትና የተፈጠርንብሽ ብለው መጥራታቸው ለእውነት የቀረበ እንጂ ስሕተት አይደለም። ይህን በመሰለችሁ በመረዳት ላይ በተመሠረተችሁ የዋህትን ገንዘብ ባደረገች የእናቶቻችንና የአባቶቻችን ንጽህት ሃይማኖት እናምናለን እንታመናለን !።

ዋቢ :- #ተአምረ ማርያም መቅድም ዘዘወትር
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥቅምት 10/2015 ዓ.ም
#ደስ ይበልሽ#

-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።

-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።

- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።

- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።

"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)

- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።

-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"

-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።

#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!

-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!

#ኢዮብ ክንፈ

#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም