#በዓለ_ቁስቋም_ዘፀአት
በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስደት የቅዱሳን የጻድቃን ሠማዕታት ፡የመነኵሳት ባህታዊያን፡የካህናት የዲያቆናት፡የምዕመናን ፡የደናግላን ስደት የተባረከበት የተቀደሰበት ወቅት የእመቤታችን ስደት አምላክ ሲሆን እንደሰው የተሰደደ ፡ የሁሉ መጠጊያ የሆነ እርሱ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የተጠጋ ወልደ አብ ወልደ ማርያም የሚታወስበት የሚዘከርበት ወርኀ ጽጌ እነሆ ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የሚለው ትንቢት የተፈፀመበት እንዲሁ በወንጌሉም
"የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ።" ተብሎ ስደቱ የተፈፀመበት ነው፡፡ የማቴ 2: 20
በወንጌሉ እንደተፃፈ እናትና ልጁ መጠለያ የነበረች ኢትዮጵያ ከጉያዋ በወጡ ልጆቿ በነበረችበት ቦታ ስደት ውስጥ ናት እና እናትና ልጇ ህዝቧን ከእንግልት አብያተክርስቲያናትን ከእሳት ምእመናንን ከሰይፍ ጠብቀው ዘፀአት እንዲሆንላት እንፀልያለን እንለምናለን መልካም በዓል፡፡
አዘጋጅ ወንድማችን #ማርቆስ_ዓለማየሁ
መዝሙር በዘማሪ #ክብሮም_ግደይ
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስደት የቅዱሳን የጻድቃን ሠማዕታት ፡የመነኵሳት ባህታዊያን፡የካህናት የዲያቆናት፡የምዕመናን ፡የደናግላን ስደት የተባረከበት የተቀደሰበት ወቅት የእመቤታችን ስደት አምላክ ሲሆን እንደሰው የተሰደደ ፡ የሁሉ መጠጊያ የሆነ እርሱ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የተጠጋ ወልደ አብ ወልደ ማርያም የሚታወስበት የሚዘከርበት ወርኀ ጽጌ እነሆ ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የሚለው ትንቢት የተፈፀመበት እንዲሁ በወንጌሉም
"የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ።" ተብሎ ስደቱ የተፈፀመበት ነው፡፡ የማቴ 2: 20
በወንጌሉ እንደተፃፈ እናትና ልጁ መጠለያ የነበረች ኢትዮጵያ ከጉያዋ በወጡ ልጆቿ በነበረችበት ቦታ ስደት ውስጥ ናት እና እናትና ልጇ ህዝቧን ከእንግልት አብያተክርስቲያናትን ከእሳት ምእመናንን ከሰይፍ ጠብቀው ዘፀአት እንዲሆንላት እንፀልያለን እንለምናለን መልካም በዓል፡፡
አዘጋጅ ወንድማችን #ማርቆስ_ዓለማየሁ
መዝሙር በዘማሪ #ክብሮም_ግደይ
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#በዓለ_ቅዱስ_ገብርኤል
❝... እግዚአብሔር በእርግጥ ያድነናል ..❞
—2ኛ ነገሥት 18: 30
ይህ ዕለት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ኢየሉጣንና ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን ከሚነድ ዕቶን እሳት ያዳነበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡
ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም ሲሆን አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ፡፡ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ወገን ናት፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ20 ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክንያት ‹‹የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ አብያተ ክርስቲያናት ይዘጉ›› ብሎ አሳወጀ፤ በዚህ ጊዜ ግማሾቹ ተሰደዱ ቅድስት ኢየሉጣም ልጇ የ3 ዓመት ሕፃን ነበርና ለርሱ ብላ ወደ ኢቆንዮን ሸሸች፡፡
በዚያም
ሀገረ ገዢው። :- ‹‹ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ›› ቢላት
እርሷም: - ‹‹ዓይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም›› ብላ መለሰችለት፡፡
እርሱም መልሶ :- ‹‹እምቢ ካልሽ በሰይፍ እቀጣሻለሁ›› ብሎ ቢያስፈራራትም
እርሷ ግን :- ‹‹ይህን ሕፃን ጠይቀው›› አለችው፡ከዚያም
ሕፃኑን :- ‹‹ወርቅ እሰጥሃለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ›› አለው፡፡
ሕፃኑ ቂርቆስ መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ‹‹ራሳቸውን እንኳ ማዳን ለማይችሉ ጣዖታትህ አልሰግድም›› ብሎ በመለሰለት ጊዜ ንጉሡ ተበሳጭቶ ‹‹በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው›› ብሎ አዘዘ፡፡
የውኃው መፍላት እንደ ክረምት ነጎድጓድ 42 ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር፡፡ የንጉሡ አገልጋዮች ሊከቷቸው ሲወስዷቸው የቅድስት ኢየሉጣ ልቧ በፍርሃት ታወከባት፤ ቅዱስ ቂርቆስ ግን የእናቱን ፍርሃት እንዲያርቅላት ይጸልይ ነበር፤ እርሷንም ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ፣ ጨክኚ፤ አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤልን ያዳነ እኛንም ያድነናል›› በማለት እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ፡፡
ከዚህ በኋላ ቅድስት ኢየሉጣ ጨክና በፍጹም ልብ ሆነው ተያይዘው ከእሳቱ ገብተዋል፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅድስት ኢየሉጣ እና ቅዱስ ቂርቆስ በወጡም ጊዜ ልብሳቸውና ሰውነታቸው ሳይቃጠል ተመልክተው ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ከሚፈላ ውኃ ያወጣቸው ሐምሌ 19 ቀን ሲሆን ሰማዕትነት የተቀበሉት ግን ጥር 15 ቀን ነው።
የቅድስት ኢየሉጣ እና የቅዱስ ቂርቆስ በረከታቸው ይደርብን
ሀገራችን ኢትዮጲያ ከሚነደው እሳት መልአኩን ልኮ ይጠብቅልን ! ላዘኑ ሰዎች መጽናናትን ያድልልን።
#ስለ_ሀገር_መጸለይን_አታስታጉሉ !
ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
18/11/2014 ዓ.ም
❝... እግዚአብሔር በእርግጥ ያድነናል ..❞
—2ኛ ነገሥት 18: 30
ይህ ዕለት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ኢየሉጣንና ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን ከሚነድ ዕቶን እሳት ያዳነበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው፡፡
ቅዱስ ቂርቆስ ሀገሩ ሮም ሲሆን አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ፡፡ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ወገን ናት፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ20 ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክንያት ‹‹የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ አብያተ ክርስቲያናት ይዘጉ›› ብሎ አሳወጀ፤ በዚህ ጊዜ ግማሾቹ ተሰደዱ ቅድስት ኢየሉጣም ልጇ የ3 ዓመት ሕፃን ነበርና ለርሱ ብላ ወደ ኢቆንዮን ሸሸች፡፡
በዚያም
ሀገረ ገዢው። :- ‹‹ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ›› ቢላት
እርሷም: - ‹‹ዓይን እያለው ለማያይ ጆሮ እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም›› ብላ መለሰችለት፡፡
እርሱም መልሶ :- ‹‹እምቢ ካልሽ በሰይፍ እቀጣሻለሁ›› ብሎ ቢያስፈራራትም
እርሷ ግን :- ‹‹ይህን ሕፃን ጠይቀው›› አለችው፡ከዚያም
ሕፃኑን :- ‹‹ወርቅ እሰጥሃለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ›› አለው፡፡
ሕፃኑ ቂርቆስ መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ‹‹ራሳቸውን እንኳ ማዳን ለማይችሉ ጣዖታትህ አልሰግድም›› ብሎ በመለሰለት ጊዜ ንጉሡ ተበሳጭቶ ‹‹በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው›› ብሎ አዘዘ፡፡
የውኃው መፍላት እንደ ክረምት ነጎድጓድ 42 ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር፡፡ የንጉሡ አገልጋዮች ሊከቷቸው ሲወስዷቸው የቅድስት ኢየሉጣ ልቧ በፍርሃት ታወከባት፤ ቅዱስ ቂርቆስ ግን የእናቱን ፍርሃት እንዲያርቅላት ይጸልይ ነበር፤ እርሷንም ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ፣ ጨክኚ፤ አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤልን ያዳነ እኛንም ያድነናል›› በማለት እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ፡፡
ከዚህ በኋላ ቅድስት ኢየሉጣ ጨክና በፍጹም ልብ ሆነው ተያይዘው ከእሳቱ ገብተዋል፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅድስት ኢየሉጣ እና ቅዱስ ቂርቆስ በወጡም ጊዜ ልብሳቸውና ሰውነታቸው ሳይቃጠል ተመልክተው ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ከሚፈላ ውኃ ያወጣቸው ሐምሌ 19 ቀን ሲሆን ሰማዕትነት የተቀበሉት ግን ጥር 15 ቀን ነው።
የቅድስት ኢየሉጣ እና የቅዱስ ቂርቆስ በረከታቸው ይደርብን
ሀገራችን ኢትዮጲያ ከሚነደው እሳት መልአኩን ልኮ ይጠብቅልን ! ላዘኑ ሰዎች መጽናናትን ያድልልን።
#ስለ_ሀገር_መጸለይን_አታስታጉሉ !
ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
18/11/2014 ዓ.ም
❤ #በዓለ_ወልድ❤
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from Eyob kinfe
❤ "ሕይወትን በሚሰጥ አዳኝ በሆነ ከአብ በሠረጸ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን" (ጸሎተ ሃይማኖት)❤
#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።
#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።
#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።
#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።
#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።
#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።
#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።
#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።
#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።
#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።
#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።
#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።
#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።
#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።
#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ኖላዊ ወበግዕ#(እረኛም በግም)
#ትጉህ #እረኛችን #አማኑኤል ከድንግል #ማርያም ተወልዶ በበረት ተኛ።ቅዱስ ዳዊት “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”(መዝ 121፥4) ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ በበረት ውስጥ ተኛ።(ሉቃ 2:7)
#እረኛ ሲሆን በግ ፣ በግ ሲሆን እረኛ ነው።መልአኩም በጎቹን (ምዕመናንን) ተግቶ የሚጠብቅ የጌታን ልደት ያበሠረው መንጎቻቸውን ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች ነው።በእረኛነቱ ይጠብቀናል ፤ በበግነቱም በመስቀል ላይ ተሠውቶልናል (ዮሐ 1:29)።
#የጌታችን እረኛነት ግን ልዩ ነው።እረኛ በጎቹን አስብቶ ኋላ ይበላቸዋል ወይም ሽጧቸው ጥቅም ያገኛል።ይህ እረኛችን ግን ስለ ራሱ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
(ዮሐ 10፥11) ሲል ተናግሯል።
#እርሱ ከሚገኝባት የበጎች በረት (ከቤተክርስቲያን) ያልሆኑ ሌሎች በጎችን አስመልክቶ ሩኅሩኅ እረኛ #መድኃኔዓለም እንዲህ ይላል “ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”(ዮሐ 10፥16)
#በዓሉን አከባበራችን ሁሉ የተዘክሮተ #እግዚአብሔር ሊሆን ይገባዋል።ስንበላ እውነተኛ መብላችን ክርስቶስ መወለዱን ፤ ስንጠጣም እውነተኛ መጠጣችን አምላካችን መወለዱን ፤ ስንለብስ ስናጌጥም እውነተኛ ልብሳችን ክርሰቶስ መወለዱን ልናስብ ይገባናል።ይህ ካልሆነ ግን ጌታ ለእኛ ያደረገውን ውለታ የዘነጋን ውለተ ቢሶች እንሆናለን።
በዓሉን በዓል የሚያደርገውም የጌታን የፈቃድ ተዋርዶውንና ውለታውን እያሰብን ካመሰገንን ብቻ ነው ፤ እንጂ የምግብና መጠጡ ጉዳይ አይደለም።ይህን #የጌታችን ውለታ ከሚያረሳሱ የቴሌቪዥን መርኃግብሮችን ሁሉ ልንጠነቀቅም ይገባናል!!!
#በዓለ #ልደቱን በተዘክሮ እግዚአብሔር እንድናከብር አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን!!!
#በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ
#ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ!!!
ልደተ #እግዚእ / 2017 ዓ.ም
#ትጉህ #እረኛችን #አማኑኤል ከድንግል #ማርያም ተወልዶ በበረት ተኛ።ቅዱስ ዳዊት “እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም።”(መዝ 121፥4) ሰው ሆኖ በሕፃናት ልማድ በበረት ውስጥ ተኛ።(ሉቃ 2:7)
#እረኛ ሲሆን በግ ፣ በግ ሲሆን እረኛ ነው።መልአኩም በጎቹን (ምዕመናንን) ተግቶ የሚጠብቅ የጌታን ልደት ያበሠረው መንጎቻቸውን ተግተው ይጠብቁ ለነበሩ እረኞች ነው።በእረኛነቱ ይጠብቀናል ፤ በበግነቱም በመስቀል ላይ ተሠውቶልናል (ዮሐ 1:29)።
#የጌታችን እረኛነት ግን ልዩ ነው።እረኛ በጎቹን አስብቶ ኋላ ይበላቸዋል ወይም ሽጧቸው ጥቅም ያገኛል።ይህ እረኛችን ግን ስለ ራሱ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
(ዮሐ 10፥11) ሲል ተናግሯል።
#እርሱ ከሚገኝባት የበጎች በረት (ከቤተክርስቲያን) ያልሆኑ ሌሎች በጎችን አስመልክቶ ሩኅሩኅ እረኛ #መድኃኔዓለም እንዲህ ይላል “ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”(ዮሐ 10፥16)
#በዓሉን አከባበራችን ሁሉ የተዘክሮተ #እግዚአብሔር ሊሆን ይገባዋል።ስንበላ እውነተኛ መብላችን ክርስቶስ መወለዱን ፤ ስንጠጣም እውነተኛ መጠጣችን አምላካችን መወለዱን ፤ ስንለብስ ስናጌጥም እውነተኛ ልብሳችን ክርሰቶስ መወለዱን ልናስብ ይገባናል።ይህ ካልሆነ ግን ጌታ ለእኛ ያደረገውን ውለታ የዘነጋን ውለተ ቢሶች እንሆናለን።
በዓሉን በዓል የሚያደርገውም የጌታን የፈቃድ ተዋርዶውንና ውለታውን እያሰብን ካመሰገንን ብቻ ነው ፤ እንጂ የምግብና መጠጡ ጉዳይ አይደለም።ይህን #የጌታችን ውለታ ከሚያረሳሱ የቴሌቪዥን መርኃግብሮችን ሁሉ ልንጠነቀቅም ይገባናል!!!
#በዓለ #ልደቱን በተዘክሮ እግዚአብሔር እንድናከብር አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይርዳን!!!
#በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ
#ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ!!!
ልደተ #እግዚእ / 2017 ዓ.ም