ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
📢ዓውደ ምህረት🎤

ውድ የዓውደ ምህረት ታዳሚዎቻችን ነገም በወንድማችን #በሙሖዘ ጥበባት በዲያቆን ዳንኤል ክብረት "#መንፈሳዊ አገልግሎት" በሚል ርዕስ እንማማራለን::



የነገ ሰው ይበለን ሰለ ሁሉም የልዑል እግዚአብሔር ስም ከእናቱ #ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል #ማርያም ጋር እና ከወዳጆቹ #ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር የከበረ የተመሰገነ ይሆን ለዘለዓለሙ አሜን❤️


ለማንኛውም ሀሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥቆማ ካለ በ @YeawedMeherte ላይ ያድርሱን::
📢📢📢📢📢📢📢
📢 #ዓውደ_ምህረት 📢
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤

ውድ የዓውደ ምህረት ታዳሚዎቻችን እንደምን ከረማችሁልን የሰላም አለቃ የፍጥረታት ምንጭ ልዑል #እግዚአብሔር ከእናቱ #ከእመቤታችን_ከቅድስት_ድንግል_ማርያም ጋር እና #ከሁሉ_ቅዱሳን ጋር ስሙ የከበረ የተመሰገነ ይሁን አሜን🙏

ውድድሮቻችንን እንደ #እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ጨርሰናል በመሆኑም በተሰጡት ትክክለኛ ምላሾች መሠረት

#ከስምቱ ኮርሶች ስምንቱንም ያለ ምንም ስእተት የመለሳችሁ🎓👈ይህን ምልክት ወይም (1) ብለው ላኩልን::


#ከስምንቱ ኮርሶች መካከል #6ኮርሶችን #አሥር አሥር ጥያቄ ያለ ምንም ስሕተት የመለሳችሁ :: 👈ይህን ምልክት ወይም ( 2) ብለው ይላኩልን



#ከስምንቱ ኮርሶች መካከል አራት የትምህርት ዓይነት ሰባት ሰባት ትክክለኛ ምላሾችን የመለሳችሁ 💟👈ይህን ምልክት ወይም (3)ብለው ይላኩልን::

ምልክቶቹን ለመላክ
#የአንድ_ሳምን_የጊዜ ገደብ እንዳለው ለማሳወቅ እንወዳለን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ወይም
@abenma
@abenma
ላይ ይላኩልን

ሲሲልኩልን የእርሶን ወይም ኢትዮጲያ አዲስ አበባ የሚገኙ የወኪሎን ከነ ሙሉ #አድራሻዎ ማለትም
#ሙሉ ስም #የሚኖሩበት_ሀገር #ስልክ #የፖስታ_ሳጥን_ቁጥር

#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
አንድም ሁለትም ለመለሳችሁና በደንብ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ #የሕይወትን_ቃል_ያሰማችሁ በዕድሜ በጤና ይጠብቃችሁ የነፍስ ዋጋ ያድረርግላችሁ!!!አሜን🙏

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
መልካም ዕድል
#የነገረ_ድኅነት ጥያቄ #መልሶች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ሐሰት
#ምክንያቱም :-ሰው ለመዳን ከማመን ያለፈ የተግባር ሰው (ምግባራትን እና ምሥጢራትን የሚፈጽም) መሆን አለበት:: ምግባራት የሚባሉትም በዋናነት #ጾም #ጸሎት #ስግደት #ምጽዋት ሲሆኑ ምሥጢራቱም #ምሥጢረ_ሜሮን #ቅዱስ_ጥምቀት እና #ቅዱስ_ቁርባን ይጠቀሳሉ #ሃይማኖት ያለ #ምግባራት ጥቅም አልባ የሞተ ነው::
"፤ ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ እንዲሁ ደግሞ #ከሥራ (ከምግባራት )የተለየ እምነት የሞተ ነው።" (የያዕቆብ መልእክት 2: 26)


#ኛ ሐሰት

#ምክንያቱም :-በተለየ አካሉ #ከእመቤታችን ከቅድስት #ድንግል_ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሶ ነፍስን ተስቶ በፍጽም ተዋህዶ #ተወልዶ ያዳነን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና:: #በምስጢረ ሥላሴ ትምህርታችን #አብ አባት #ወልድ ልጅ #መንፈስ ቅዱስ ሰራፂ ብለን ተምረናል እንዲህም እናምናለን:: ቅዱሳት መጻሕፍትም በተዋህዶ ተወልዶ ያዳነን ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በስፋት ይነግሩናል:: ለምሳሌ "እግዚአብሔር አንድያ #ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶልና" ዮሐ3÷16

#ኛ ሐሰት

#ምክንያቱም :- ምንም እንኳን ድኅነት በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ አንድ ጊዜ ተፈጽሞ ለሰው ልጆች የተሰጠ ቢሆንም ከዚህ ከተሰጠው ድኅነት ግን ለመካፈል ሰው የራሱን ጥረት ማድረግ ይገባዋል። ድኅነት በእግዚአብሔር ዘንድ የተፈጸመ ስለሆነ ብቻ ሰው ሁሉ ያመነውም ያላመነውም በግዴታ ይድናል ማለት አይደለም:: ለመዳን የወደደ ብቻ ከተፈፀመለት የድኅነት ሥራ በምግባራት ተሳትፎ ድኅነትን ያገኛል:: ስለዚህ በድኅነት ውስጥ ሰውም ሊፈጽመው የሚገባ ሂደት ነው::
"፤ ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ #እንደ_ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ #የራሳችሁን_መዳን_ፈጽሙ፤"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2: 12)

ልናስተውለው የሚገባን #የታዘዛችሁትን_በመፈጸም የምትለዋ እና #የራሳችሁን_መዳን_ፈጽሙ የምትለዋን ነው

በመሆኑም የእራሳችንን መዳን መፈጸም የምንችለው እና ከተሰራልን የድኅነት ሥራ የምንካፈለው የታዘዝነውን በመፈፀም ነው:: #የታዘዝነውም 10ቱ ትዕዛዛት 6ቱ ቃላተ ወንጌል ናቸው እነዚህን ለመፈፀም ደግሞ ጊዜ ዘመን ያስፈልገናል:: ይህ ደግሞ ድኅነት በሂደት የሚፈፀም እንጂ በአንድ ቀን በአንድ ቦታ በሰዓት ጌታን በመቀበል ብቻ አለመሆኑን ያስገነዝበናል:: በጥቅሉ ለመዳን ሰው የራሱ ድርሻን መወጣት ይገባዋል።

#ኛ እውነት

#ኛ ሐሰት
ምክንያቱም:-ያልተመለሰለት ጸጋ የለምና::
ፀጋ:-
ልጅነትን:- ከእንግዲ ወዲ ባሮች አትባሉም
ወራሽነትን:-
ገዢነትን(ሥልጣንን):- ግዛ ንዳ የተባለሁ ዓለምና በዓለም ያሉትን ነገሮች ሁሉ ዛሬም ሰው ከትዕዛዙ ካልራቀ ሕጉን ከጠበቀ ከተፈጥሮ ሁሉ በላይ መግዛት መንዳት የሚችልና ሥልጣኑ ያለው መሆኑን በቅዱሳን ሕይወት መመልከት ይቻላል::


#በአጭሩ መልሱ

#ኛ #ስለ_ፍጽም_ፍቅሩ
#ለካሳ ለቤዛ
#የዲያብሎስ ጥበብ #በጥበቡ #ለመሻር
#ለምሳሌነት_ለአራያነት
#ድኅነት ሥርዓት ስላለው…

#ኛ #ማመን
#ሥራ (ምግባራት)
#ምሥጢራትን መፈጸም ማር 16:16 ዮሐ 6:54


#ኛ "፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ #በእርሱም ቍስል #እኛ ተፈወስን።"

(ትንቢተ ኢሳይያስ 53: 5)
"፤ #እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ #ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም #የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።"
(ትንቢተ ኢሳይያስ 53: 6)

ነብዩ ስለ እኔ ብቻ አላለም #እኛ ብሎ አብዝቶ ተናገረ እንጂ:: እኛ ብሎ አብዝቶ መናገሩ የዓለምን ኃጢያት የተሸከመ የዓለም መድኀን መሆኑን ሲገልጥ ነው::

"እነሆ #የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ #የእግዚአብሔር_በግ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1: 29)


#ኛ #መንግስቱን_ሲወርስ_ስሙን_ሲቀድስ


#ኛ ማዳን የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው ማለት እንጂ ቅዱሳን አያድኑም ወይም መድኀኒት አይባሉም ለማለት አይደለም:: በቅዱስ መጽሐፍ ሰዎች ሆነው አዳኝ ተብለው የተጠሩ አሉ #ለምሳሌ "፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ #እግዚአብሔርም_የሚያድናቸውን_አዳኝ የካሌብን የታናሽ ወንድሙን የቄኔዝን ልጅ #ጎቶንያልን_አስነሣላቸው።"
(መጽሐፈ መሳፍንት 3: 9) ይህ የሚያሳየው እግዚአብሔር ቅዱሳን ሰዎችን አዳኝ መድኀኒት አድርጎ እንደሚያስነሳ ነው:: መዳን በሌላ በማንም የለም ማለቱ የቅዱሳን አዳኝነት (መድኀኒትነት) ጠፍቶት አይደለም:: ቅዱሳን የጸጋ አዳኝ ናቸው:: ጸጋ ደግሞ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ፣የተቸረ ፣የተለገሰ ስጦታ ማለት ነው:: ስለዚህ ቅዱሳን መድኀኒት ቢባሉ በስጦታ ያገኙት ነው። "#እድንበት ዘንድ ከሰማይ በታች የተሰጠን #ሌላ ስም የለም" ማለቱ ደግሞ ቅዱሳን ሲያድኑም በእራሳቸው ኃይል ሳይሆን ማዳንን በሰጣቸው በፈጣሪያቸው ስም ነው ማለቱ ነው:: ቅዱሳን መላእክት አዳኝ (መድኅኒት )ናቸው። ስማቸው ስመ እግዚአብሔር ተሸክሞልና:: ስለሆነም ቅዱስ ሚካኤል አዳነ ማለት እግዚአብሔር አደነ ማለት ነው ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ (ቅዱሳን ሰዎችም) ቢያድኑ የፈጣሪን ስሙን ጠርተው ነው "፤ ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ #በናዝሬቱ_በኢየሱስ_ክርስቶስ_ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።"
(የሐዋርያት ሥራ 3: 6)
ከዚህም ባሻገር ቅዱሳን ወደ ቅድስና ሲጠሩ ስማቸው ይለወጣል ስመ እግዚአብሔርም ይሆናል:: በመሆኑ እነርሱም በስማቸው ማዳን ይቻላቸዋል "፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ #በእኔ_የሚያምን_እኔ_የማደርገውን_ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ #ከዚህም_የሚበልጥ_ያደርጋል፥" (የዮሐንስ ወንጌል 14: 12)
ከእርሱ አብልጦ የሚሰራ የለም ነገር ግን በስሙ ላመኑ እርሱ ያደረገውን ሁሉ የማድረግ ሥልጣን አላቸው ማለቱ ነው።

ይቆየን።

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#ከጸሎተኛው_አፍ_በሚወጣ_አበባ ያመኑ ሽፍቶች
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ከሮም ነገሥታት ወገን የሆነ ስሙ ዘካሪያስ የሚባል ጎልማሳ ሰው ነበር ከዕለታት አንድ ቀን #ቤተ_ክርስቲያን ገብቶ #ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ሲጸልይ ከሥዕሏ ማማር የተነሳ እጅግ ደስ አለውና ለዚህች ሥዕል ምን ዐይነት እጅ መንሻ ላቅርብላት እያለ ሲያወጣና ሲያወርድ ወራቱ የጽጌ ጌዳ ወራት ነበርና ፶ (50) የጽጌ ጌዳ አበባ ወስዶ ዘውድ አስመስሎና አክሊል ሰርቶ ከሥዕሏ እራስ ላይ ወስዶ በክብር አቀዳጃት ይህ ሰው እንዲ እያደሰገ ሲጸልይ ከቆየ በኃላ የጽጌ ወራት ባለፈ ጊዜ ግን ለሥዕሏ ክብር የሚያቀርብላት የጽጌ ሬዳ አበባ በማጣቱ እጅግ አዝኖ ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሄደና #እመቤቴ ሆይ የጽጌ ሬዳ፣ የአበባ ወራት እንዳለፈ አንቺ ታውቂያለሽ በ፶ (50)ው የጽጌ ሬዳ አበባ ፈንታ (ምትክ) ፶ (50)ጊዜ #በሠላመ_ቅዱስ_ገብርኤልን የሚለውን ጸሎትሽን ወይም ሠላምታሽን እጸልያለው በማለት እንዲ አለ " #እመቤቴ_ማርያም_ሆይ_በመላእኩ_በቅዱስ_ገብርኤል_ሠላምታ_ሠላም_እልሻለሁ_እግዚአብሔር_ካንቺ_ጋር_ነውና_ደስ_ይበልሽ " እያለ በየቀኑ ፶ (50) ጊዜ ሲጸልይ ኖረ ።
ከዕለታት አንድ ቀን ግን እረስቶ ይህችን ጸሎት ሳያደርስ መንገድ ጀመረ በመንገድም እያለ ይህችን ጸሎት አለማድረሱ ታወሰውና ጉዞውን ገታ አድርጎ ከመንገድም ወጣ ብሎ እንደ ቀድሞው እየሰገደ ሠላምታዋን ፶ (50) ጊዜ በጸሎት ማድረስ ቀጠለ ሲጸልይም ከአፉሁ በእያንዳንዱ ሠላምታ አንድ አንድ ጽጌ ሬዳ አበባ ይወጣ ነበር። #እመቤታችንም አበባው ፶ (50) እስኪሞላ ድረስ ከአፉሁ እየተቀበለች በክንዷ ሰብስባ ትታቀፈው ነበር :: በአካባቢው የነበረ የሽፍቶች አለቃ የሆነ አንድ ሰው ይህንን አይቶ ዘካሪያስ ጸሎቱን እስኪ ጨርስ ድረስ ከአፉሁ የሚወጡትን የጽጌ ሬዳ አበቦች ይቆጥር ጀመር። ዘካሪያስም ጸሎቱን ሲጨርስና አበባዎቹም ፶ ሲሞሉ #እመቤታችን ባርካው አበባዎቹን ይዛ ወደላይ ስታርግ ይህ የሽፍቶች አለቃ አይቶ እጅግ አደነቀና ጓደኛቱይ ጠርቶ " የጌታን ተአምራት ታዮ ዘንድ ኑ " ተብሎ እንደ ተጻፈ "የእመቤታችንን ተአምራት ያዮ ዘንድ ኑ " ብሎ ወደ ዘካሪያስ ወሰዳቸው መዝ 45÷8 ሽፍቶቹም ዘካሪያስን ይህ ድንቅ ተአምራት ምንድ ነው? ብለው ጠየቁት እርሱም እኔ ኃጢያተኛ ከመሆኔ በቀር ሌላ በጎ ሥራ የለኝም ነገር ግን የሠማይና የምድር ንግሥት የሆነች አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች የእመቤታችንን በሠላመ #ቅዱስ_ገብርኤል_መላእክ ሠላም እልሻለሁ እያልኩ #በቅዱስ_ገብርኤል ሙሉ ሰላምታ በየ ቀኑ ፶ ( 50)ጊዜ ሠላም እላታለሁኝ አላቸው በዚህ ጊዜ ደስ ብሏቸው ዘካሪያስን ሸኙት እነርሱም ከዛች ቀን ጀምሮ ከክፉሁ ሥራቸው ተመልሰው ወደ ገዳም ሄደው በምንኩስና ሕይወት ተወስነው መኖር ጀመሩ::
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ምንጭ:-
በምሥራቅ ጎጃም ሞጣ ደብረ ገነተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያለ የብራና ተአምረ ማርያም ገጽ 223 ጠቅሶ የጻፈው ማህሌተ ጽጌ የተሰኘው ትንሽዬ መጻሕፍ ነው
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ከጸሎተኛው_አፍ_በሚወጣ_አበባ ያመኑ ሽፍቶች
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ከሮም ነገሥታት ወገን የሆነ ስሙ ዘካሪያስ የሚባል ጎልማሳ ሰው ነበር ከዕለታት አንድ ቀን #ቤተ_ክርስቲያን ገብቶ #ከእመቤታችን ሥዕል ፊት ሲጸልይ ከሥዕሏ ማማር የተነሳ እጅግ ደስ አለውና ለዚህች ሥዕል ምን ዐይነት እጅ መንሻ ላቅርብላት እያለ ሲያወጣና ሲያወርድ ወራቱ የጽጌ ጌዳ ወራት ነበርና ፶ (50) የጽጌ ጌዳ አበባ ወስዶ ዘውድ አስመስሎና አክሊል ሰርቶ ከሥዕሏ እራስ ላይ ወስዶ በክብር አቀዳጃት ይህ ሰው እንዲ እያደሰገ ሲጸልይ ከቆየ በኃላ የጽጌ ወራት ባለፈ ጊዜ ግን ለሥዕሏ ክብር የሚያቀርብላት የጽጌ ሬዳ አበባ በማጣቱ እጅግ አዝኖ ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ሄደና #እመቤቴ ሆይ የጽጌ ሬዳ፣ የአበባ ወራት እንዳለፈ አንቺ ታውቂያለሽ በ፶ (50)ው የጽጌ ሬዳ አበባ ፈንታ (ምትክ) ፶ (50)ጊዜ #በሠላመ_ቅዱስ_ገብርኤልን የሚለውን ጸሎትሽን ወይም ሠላምታሽን እጸልያለው በማለት እንዲ አለ " #እመቤቴ_ማርያም_ሆይ_በመላእኩ_በቅዱስ_ገብርኤል_ሠላምታ_ሠላም_እልሻለሁ_እግዚአብሔር_ካንቺ_ጋር_ነውና_ደስ_ይበልሽ " እያለ በየቀኑ ፶ (50) ጊዜ ሲጸልይ ኖረ ።
ከዕለታት አንድ ቀን ግን እረስቶ ይህችን ጸሎት ሳያደርስ መንገድ ጀመረ በመንገድም እያለ ይህችን ጸሎት አለማድረሱ ታወሰውና ጉዞውን ገታ አድርጎ ከመንገድም ወጣ ብሎ እንደ ቀድሞው እየሰገደ ሠላምታዋን ፶ (50) ጊዜ በጸሎት ማድረስ ቀጠለ ሲጸልይም ከአፉሁ በእያንዳንዱ ሠላምታ አንድ አንድ ጽጌ ሬዳ አበባ ይወጣ ነበር። #እመቤታችንም አበባው ፶ (50) እስኪሞላ ድረስ ከአፉሁ እየተቀበለች በክንዷ ሰብስባ ትታቀፈው ነበር :: በአካባቢው የነበረ የሽፍቶች አለቃ የሆነ አንድ ሰው ይህንን አይቶ ዘካሪያስ ጸሎቱን እስኪ ጨርስ ድረስ ከአፉሁ የሚወጡትን የጽጌ ሬዳ አበቦች ይቆጥር ጀመር። ዘካሪያስም ጸሎቱን ሲጨርስና አበባዎቹም ፶ ሲሞሉ #እመቤታችን ባርካው አበባዎቹን ይዛ ወደላይ ስታርግ ይህ የሽፍቶች አለቃ አይቶ እጅግ አደነቀና ጓደኛቱይ ጠርቶ " የጌታን ተአምራት ታዮ ዘንድ ኑ " ተብሎ እንደ ተጻፈ "የእመቤታችንን ተአምራት ያዮ ዘንድ ኑ " ብሎ ወደ ዘካሪያስ ወሰዳቸው መዝ 45÷8 ሽፍቶቹም ዘካሪያስን ይህ ድንቅ ተአምራት ምንድ ነው? ብለው ጠየቁት እርሱም እኔ ኃጢያተኛ ከመሆኔ በቀር ሌላ በጎ ሥራ የለኝም ነገር ግን የሠማይና የምድር ንግሥት የሆነች አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች የእመቤታችንን በሠላመ #ቅዱስ_ገብርኤል_መላእክ ሠላም እልሻለሁ እያልኩ #በቅዱስ_ገብርኤል ሙሉ ሰላምታ በየ ቀኑ ፶ ( 50)ጊዜ ሠላም እላታለሁኝ አላቸው በዚህ ጊዜ ደስ ብሏቸው ዘካሪያስን ሸኙት እነርሱም ከዛች ቀን ጀምሮ ከክፉሁ ሥራቸው ተመልሰው ወደ ገዳም ሄደው በምንኩስና ሕይወት ተወስነው መኖር ጀመሩ::
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
ምንጭ:-
በምሥራቅ ጎጃም ሞጣ ደብረ ገነተ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ያለ የብራና ተአምረ ማርያም ገጽ 223 ጠቅሶ የጻፈው ማህሌተ ጽጌ የተሰኘው ትንሽዬ መጻሕፍ ነው
ኃ/ማርያም
ጥቅምት 2/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#ደስ ይበልሽ#

-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።

-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።

- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።

- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።

"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)

- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።

-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"

-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።

#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!

-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!

#ኢዮብ ክንፈ

#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም