ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
በቅድሚያ ስለ ጥያቄዎት #እናመሰግናለን🙏

መነኮሳት ቢጫ ልብስ የሚለብሱበት ምክንያት ቢጫ ብርሃናዊ ነው አንተም እንደተናገርከው ብርሃናዊ አምላክ ነክ ሲሉ ነው "፤ ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 8: 12)

#አንድም ጻድቃን በአባታቸው መንግስት እንደ ፀሐይ ያበራሉ ተብሎ እንደተጻፈው በአባታችን ቤት እንደ ፀሐይ እናበራለን ሲሉ ቢጫ ልብስን ይለብሳሉ "፤ በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 13: 43)

በሌላ መልኩ ቢጫ የብሩህነት በብሩህነትመም የተስፋ ምልክት እንደሆነ ብሩህ የሆነች መንግስትህት ታወርሰን ዘንድ ተስፋ አለን ሲሉ ይለብሱታል

"፤ በጸሎታችን ጊዜ ስለ እናንተ ስናሳስብ፥ የእምነታችሁን ስራ የፍቅራችሁንም ድካም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን #የተስፋችሁን መጽናት በአምላካችንና በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እያሰብን፥ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በሁላችሁ ምክንያት እናመሰግናለን፤"
(1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 1: 2-3)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ከዚህ ቀደም በምን እንጠይቅልዎ አምዳችን ከተጠየቁ ጥያቄዎች በወንድማችን #ተርቢኖስ_ሰብስቤ የተመለሱትን መልሶች ይዘን ቀርበናል።

#ጥያቄ
መምህር አንድ ጥያቄ ነበረኝ
መኖክሳት የሚለብሱት ብጫ ልብስ የምን ምሳሌ ነው
ወይም ብጫ ልብስ ለምን ይለብሳሉ?

#መልስ
በቅድሚያ ስለ ጥያቄዎት #እናመሰግናለን🙏

መነኮሳት ቢጫ ልብስ የሚለብሱበት ምክንያት ቢጫ ብርሃናዊ ነው አንተም እንደተናገርከው ብርሃናዊ አምላክ ነክ ሲሉ ነው "፤ ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 8: 12)

#አንድም ጻድቃን በአባታቸው መንግስት እንደ ፀሐይ ያበራሉ ተብሎ እንደተጻፈው በአባታችን ቤት እንደ ፀሐይ እናበራለን ሲሉ ቢጫ ልብስን ይለብሳሉ "፤ በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 13: 43)

በሌላ መልኩ ቢጫ የብሩህነት የተስፋ ምልክት እንደሆነ ብሩህ የሆነች መንግስትህት ታወርሰን ዘንድ ተስፋ አለን ሲሉ ይለብሱታል

"፤ በጸሎታችን ጊዜ ስለ እናንተ ስናሳስብ፥ የእምነታችሁን ስራ የፍቅራችሁንም ድካም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን #የተስፋችሁን መጽናት በአምላካችንና በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እያሰብን፥ እግዚአብሔርን ሁል ጊዜ በሁላችሁ ምክንያት እናመሰግናለን፤"
(1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 1: 2-3)

#ጥያቄ
ሰላም ለናንተ ይሁን ውድ እህት ወንድሞቸ ፍጹም በወደደና ናሰባሰበን በልዑል እግዚአብሔር ሰላም እንዴት አደራችሁ
በእውነት ለሁላችሁም ጸጋውን ያብዛላችሁ ሰማያዊ ዋጋን ይክፈልልን እኛም የሰማነውን 30 60 100 ያማረ ፍሬ አፍርተን ቃሉን እንድንማር እግዚአብሔር ይርዳን። ጥያቄ ነበረኝ ጸጋው የበዛላችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች አብራሩልኝ
1.ቃልኪዳን ማለት ምን ማለት ነው⁉️ ለምሳሌ ለጻድቃንና ለሰማዕታት የኢየሱስ ክርስቶስ የሰጣቸው ቃል ኪዳን አለ ለምሳሌ እነ ቅድስት አርሴማ ተክለ ሃይማኖት ቅዱስ ጊዮርጊስ ለነዚህና ለመሳሰሉት ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። ሁላችንም እናውቃለን ነገር ግን ምንድነው
ለመምህር ግርማና ላባ ዮሐንስ እግዚአብሔር ቃልኪዳን ሰቷቸው ነው ወይስ እግዚአብሔር ጸጋውን አድሏቸው ነው⁉️ ብዙ ሰወች እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ስለሰጣቸው ነው ይሉናል ለነዚህ አይነት ሰወች ምን መልስ መስጠት እዳለብን ብታብራሩልን?

#መልስ
ቃል ኪዳን ማለት #ውል #ስምምነት #መዕላ ማለት ነው

ሰው የሚምለው የሚዋዋለው ስምምነት የሚፈጥረው ከመረጠው ከወዳጁ ጋር ነው እንጂ ከወጪ ወራጁ #ከመንገደኛው #ሁሉ ጋር አይደለም::ልክ እንዲሁ #እግዚአብሔር አምላክም ቃል ኪዳን የሚገባው #ለመረጣቸው ሰዎች ብቻ ነው::
"#ከመረጥሁት ጋር #ቃል ኪዳኔን #አደረግሁ፥ " ብሎ እደተናገረ #መዝ 88÷3

ስለዚህ ቃል ኪዳን የተገባው ለሁሉ አይደለም ጸድቃን ቅዱሳን ቢመረጡ ከእራሳቸው ይልቅ ክርስቶስን ሰብከው ነው ::እንደ ዘመናችን አጥማቂ ነኝ ባዮች በክርስቶስ ዓውደ ምህረት ላይ ቆመው እራሳቸውን የሚሰብኩ መቁጠሪያና ሲዲ ቸብችበው አይደለም::
አጋንንት ያለ ጾምና ጸሎት በመቁጠሪያ እና በስልክ አይወጣም ዛሬ ዛሬ በስልክ አጋንንትን እናስለቅቃለን የሚሉ አሉ:: አጋንንትም ያወጣ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም
"፤ ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 17: 21)

"የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ #ጥቂቶች " "፤ የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።" (የማቴዎስ ወንጌል 22: 14) እንደተባለ የተመረጡት ቃል ኪዳን ያላቸው ከንቱ ውዳሴን የሚጠየፉት ጽላት የተቀረጸላቸው ቤተ ክርስቲያን የታነጸላቸው ገድልና ተአምር የተጻፈላቸው የጥንቶቹ እነ አቡነ #ተክለ ሃይማኖት ናቸው

የክርስቶስ ማለያ ለብሰው ለዲያቢሎስ #የሚጫወቱ አሳዊያን(አሰተኞች )በዝተዋልና በእጁጉ እንጠንቀቅ መልክታችን ነው:: "፤ ብዙዎች፦ እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 24: 5)

"፤ በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። የዚያን ጊዜም። ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።"
(የማቴዎስ ወንጌል 7: 22)

ለመጨመር ያህል ቅዱሳን ቃልኪዳንን የሚቀበሉት በከበረ ዕረፍታቸው ነው።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን ..... #ይቆየን 🙏

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
የሰሙነ ሕማማት - ሐሙስ - "የምስጢር ሐሙስ፣ የትዕትና ሐሙስ ፣ ጸሎተ ሐሙስ እና ምሴተ ሐሙስ " ትባላለች !

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እና መምህር ሲሆን የአገልጋዮቹን የሐዋርያትን እግር ዝቅ ብሎ ማጠቡ ይታሰብበታል።

#አንድም አዲስ ምስጢር በተግባር ምስጢረ ጥቅምት እና ምስጢረ ቁርባን የተመሰረቱበት ቀን ነው።

#አንድም ጌታ የመጨረሻውን ጸሎት በ ጌቴሴማኔ የጸለየበት ነው ። ለሐዋርያቱ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ ብሎ ያስተማረበት ዕለት ነው።

#አንድም ከስቅለት በፊት የምትገኝ ሐሙስ ናት እና የመጨረሻዋ ሐሙስ ትባላለች። በሲኦል ቁራኝነት ለሚኖሩ ነፍሳት የመጨረሻቸውም ናትና ።

ስለትዕትናው ግን ሊቁ እንዲህ ያመሰግናል !

ተራሮችን በኀይሉ የሚያስታጥቃቸው ለማገልገል ማበሻ ጨርቅ ታጠቀ፤ የባሕርን ውሃ እንደ አቁማዳ የሚሰበስበው በወንዞች መዝገቦች የሚሾማቸው ርሱ ከወዳጁ ከአልዓዛር ቤት የውሃ ማድጋ አንሥቶ እግሮችን ለማጠብ ያገለግልባት ዘንድ ወደ ኩስኩስት አፈሰሰ፤ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን እንዲታጠቡ የናስ ኩስኩስት ሠርቶ በኦሪቷ ድንኳን ደጃፍ እንዲያኖራት ሙሴን ያዘዘው ውሃውን በኩስኩስት ሞልቶ የደቀ መዛሙርቱን እግር ሊያጥብ ጀመረ።

መጽሀፈ ምስጢር በቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ


ጌታችን አምላካችን ራርቶ ይቅር ይለን ዘንድ ልመናችንንንም ተቀብሎ ይህችን ሳምንት በደህና ያስፈጽመን በሰላም ዘንድ የትንሳኤውንም ብርሃን በፍጹም ደስታ ያሳየን ዘንድ ኃጥያታችንንም ያስተሰርይልን ዘንድ #ጸልዩ

#እግዚኦ_ተሰሃለነ
#በሕማሙ_ይታረቀን
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ቅድስት