ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
" #የጻድቅ_መታሰቢያ_ለበረከት_ነው ፤ የኀጥኣን ስም ግን ይጠፋል።"

#ምሳሌ_10÷7
#አቡነ_ጴጥሮስ_ጳጳሰ_ዘምሥራቅ_ኢትዮጵያ_ተላዌ_አሰሩ_ለአቡነ_ኢየሱስ_ሞዓ

በ1885 ዓ/ም ፍቼ ከተማ ተወለዱ፤ የዓለም ስማቸውም፤ ኃይለ ማርያም ተባለ። በ1909 ዓ/ም መንኩሰው፤ “በ1910 ዓ/ም በወላሞ ወረዳ የደብረ መንክራት ገዳም መምህር ተብለው ተሾሙ። በ1916 ዓ/ም በዝዋይ ደሴት የገዳሙ መምህር ሆኑ። በ1921 ዓ/ም በእስክንድርያ ቅዱስ ማርቆስ ከአራት ጳጳሳት ጋር ጳጳስ ሲሆኑ ስማቸውም ጴጥሮስ ተባለ።” (ጳዎሎስ ኞኞ፤ “የኢትዮጵያና የኢጣልያ ጦርነት”፤ ገጽ 156)።

የጣልያንን ወረራ ለመከላከል በ1928 አዋጅ በታወጀ ጊዜ በወቅቱ የምስራቅ ኢትዮጵያ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ጴጥሮስ ንጉሠነገሥቱንተከትለው ወደማይጨው ዘመቱ።
#በ1928 ሐምሌ21 ቀን የተባበሩት የአርበኞች ግምባርአዲስ አበባ ላይ የሠፈረውን የጠላት ጦርለመዋጋት በአደረገው ቀጠሮ መሠረት አቡነጴጥሮሥ በነደጃዝማች አበራ ካሣ ይመራከነበረው የሰላሌ ጦር አብረው ወደ አዲስአበባ ገቡ። ይህ ጦር ግን የሚፈለገው ውጤጥ አለመምጣቱን በመገንዘብ ወደመጣበት ሢያፈገፍግ አቡነ ጴጥሮሥ የአዲስአበባን ህዝብ ሰብከው በጠላት ላይ ለማስነሳት እና ሀገሩንና ሃይማኖቱን እንዳያጣ ለማንቃት በማሰብ ከጦሩ ተለይተው አዲስ አበባ ቀሩ። ብዙም ሳይቆዩ አንድ ቀን ብቻ እንደቆዩ ተይዘው የጦር አለቆች ፊት ቀረቡ።

ብፁእነታቸው ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ በጠላት የጥይት እሩምታ እስከተገደሉበት ጊዜ ድረስየነበረውን ሂደት 'ኮርየር ዴላሴራ' (corrieredella sera) የተባለው ጋዜጣ ወኪል እና የምስራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕል አዘጋጅ የነበረው 'ፖጃሌ' የተባለ ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ. ሰኔ 15ቀን 1936 ዓም አዲስ አበባ በነበረ ጊዜሂደቱን ባየውና በተመለከተው መንገድ እንደሚከተለው ፅፎ ነበር
"ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም ፊታቸውም ዘለግ ያለና መልካቸው ጠየም ያለ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ፡፡ ለፍርድም የተሠየሙት ዳኞች ሦስት ሲሆኑ እነዚህም ጣሊያኖችና የጦር ሹማምንት ናቸው፡፡ የመካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር፡፡ የቀረበባቸውም ወንጀል 'ሕዝብ ቀስቅሰዋል፣ ራስዎም ዐ ምፀዋል፣ ሌሎችንም አንዲያምፁ አድርገዋል' የሚል ነበር፡፡ ዳኛውም 'ካህናቱም ሆኑ የቤተ ከህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቂርሎስም የኢጣሊያንን መንግሥት ገዢነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ አርስዎ ለምን ዐመፁ፣ ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?' ሲል ጠየቃቸው ፡፡ #አቡነ_ጴጥሮስም የሚከተለውን #መለሱ''፡፡
#አቡነ_ቄርሎስ_ግብፃዊ ናቸው፣ #ስለ_ ኢትዮጵያና_ኢትዮጵያውያን_የሚገዳቸው_ነገር የለም፡፡#አኔ_ግን_ኢትዮጵያዊ_ነኝ፡፡ #አላፊነትም_ያለብኝ_የቤተ_ክርስቲያን_አባት_ነኝ፡፡ ስለዚህ #ስለ_ሀገሬና_ስለ_ቤተ_ክርስቲያኔ _አቆረቆራለሁ፡፡ ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም፡፡ #ለፈጣረዬ_ብቻ _የምናገረውን አናገራለሁ፡፡ #እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ #ስለዚህ_በእኔ_ላይ_ _የፈለጋችሁትን_አድርጉ፡፡ #ግን_ተከታዮቼን_አትንኩ' አሉ፡፡
ይህንንም ብለው በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ እንዲያይ ተጋብዞ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚከተለውን ሕያው መልእከት አስተላለፉ፡፡
'#'አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት #ቤተክርስቲያንን_ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው፡ #እንጂ በጎ ለመሥራት፣ እውነተኛ ፍርድ ለመስጠት ስላልመጣ #ለዚህ_ለግፈኛ_አትገዙ !!!፡፡ ስለ ውድ #ሀገራችሁ፣ ስለ ቀናች #ሃይማኖታችሁ_ተከላከለ
#ነጻነታችሁ_ከሚረክስ_ሙታቹህ_ስማችሁ_ሲቀደስ_ታላቅ_ዋጋ_ያለው_ክብር_ታገኛላችሁ#የኢትዮጵያ_ሕዝብ ለዚህ ለጠላት #እንዳይገዛ_አውግዣለሁ_የኢትዮጵ_መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን። #በፈጣሪየ_በኢየሱስ_ክርስቶስ_ስም_የተገዘተች ትሁን።''

#አባታችን_ብጹዕ_አቡነ_ጴጥሮስ _ሐቀ _ነበሩ። ነገር ግን ለኢጣሊያ ለጋስዮን ታዝዞ የመጣው አስተርጓሚ ዳኞች የሚሉትን ብቻ ከማስተርገ፡ም በቀር አባታችን የሚናገሩትን ሐቀኛ ንግግር አላስተረጎመም፡፡ አኔ እንኳን የሰማሁት በአዲስ አበበ ለሠላሳ ዓመት የኖረው የእቴጌ ሆቴል ሐላፊ የነበረው የግሪክ ዜጋ ማንድራኮስ አጠገቢ ተቀምጦ ስለ ነበር የተናገሩትን ሁሉ ስለ ገለጠልኝ ነው፡፡ እኔ እንደ ሰማሁት ፍርዱን ለመስማት በብዛት የተስበስቡት ጣሊያኖችና ታዝዞ የወጣው የአዲስ አበበ ሕዝብ ሐቀኛ የሆነውን ንግግራቸውን ቢሰማ ኖሮ ልባቸው ይነካ ነበር"።
ሆኖም አስተርጓሚው በጳጳሱ ላይ ተጽዕኖ ስላሳደረበቸው እውነተኛ ንግግራቸው ሳይገለጥ ቀረ። ቀጥሎም ብፁእነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለ ርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያው የሞታቸው ፍርድ ሲሰማ ሕዝቡ በኢጣልያ የእጅ ሰላምታ ዓይነት እጁን እንዲያነሣ ታዘዘ። በዚያን ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ስዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣሊያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር፡፡ ታላቅ ፍርሃትም በፈቱ ላይ ይታይ ነበር።
ይሙት በቃ የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉኖ ደከሞአቸው ስለ ነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠየቁት። እንዲ ቀመጡም ፈቀደላቸው፡፡ በመጨረሻም የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኩዋቸው። ብፁዕነታቸው እስከ መቃብር አፋፍ ድረስ የፍርሃትና የድንጋጤ ምልክት ያይደለ ከልብ የሆነ ፍጹም ቆራጥነት ይታይባቸው ነበር፡፡
የሀገራቸው በጠላት መወረር የሕዝበቸው መገደልና መታስር የቤተ ከርስቲያናቸው መደፈር እስከ ሞት ያደረሳቸው እኒህ እውነተኛ ጳጳስ ለመገደል ሊወስዱ ጥይት አልፎ ሌላ ስው እንዳይጎዳ ግንብ ይፈለግ ጀመር፡፡ ሩቅ ባለመሔድ ከመካነ ፍትሑ 10 ሜትር ርቆ ግንብ ያለው መግደያ ቦታ ተገኘና ወደዚያ ተወስዱ። ከገዳዮቹም አንዱ 'ፊትዎን ለመሸፈን ይፈልጋሉገ?' ሲል ጠየቃቸው፡፡ 'ይህ የአንተ ሥራ ነው' ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ'፡፡ ከመግደያውም ቦታ እንደ ደረሱ ወንበር ቀረበላቸውና ፊታቸውን ወደ ግንቡ ጀርባቸውን ወደ ሕዝቡ እድርገው እንዲቀመጡ ሆኑ።
ከዚያ በኋላ ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ ርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተጠንቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ 'ተኩስ' በማለት ትእዛዝ ሲስጥ ስምንቱም ተኩስው መቱዋቸው። ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ። መሞታቸውንና አላመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ። ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ። ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው፡፡
የብፁዕነታቸው አሰክሬን ማንም እንዳይወስደው በአስቸኳይ ከአዲስ አበባ ውጭ ማንም በማያውቀው ቦታ በምሥጢር አንዲቀበር ተደሪገ። በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ" በተጨማሪም ደራሲና ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ "አቡነ ጴጥሮስ እንዴት ሞቱ" ሲል ሙሴ ፓይላክን ጠይቆአቸው እርስቸውም

የሚክተለውን ተናግረዋል። "አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ። መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳ ቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት
" #አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል"
" #መስቀሌን በመስቀልያ ቦታ አስቀምጥ"
መጽሐፈ #ጤፉት


መስቀሌን በመስቀልያ ቦታ አስቀምጥ የሚለው ትዕዛዝ ለአፄ ዘር ያዕቆብ የተነገረ ቢሆንም ቅሉ ለኛ ለክርስቲያኖችም የታዘዘ ኃይለ ቃል ነው። የሰው ልጅ ቃጥ ብሎ ቆሞ እጆቹን ወደ ግራና ወደ ቀኝ ቢዘረጋ ሁነኛ የመስቀል ቅርጽ ያለው መስቀልያ ቦታ መሆኑን ይረዳ ነበር። ብዙዎች ግን በprotocol ሰበብ ለቀረጻ አይመችም !፣ ለሰርግ አይሆንም ፣ ውበት ይደብቃል እያሉ መስቀሉን ከመስቀልያ ቦታ አውርደው ጥለውታል። ቅዱስ መስቀሉ ግን "እንወደው ዘንድ ደም ግባት የለውም" ኢሳ53÷1-12 እስኪባልለት ድረስ መዳኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ደም ግባት ያለን ያደርገን ዘንድ ወዝና ደሙን ያንጠፈጠፈበት ውበታችን ነበር ። #ስለዚህ_ዛሬም "አንብሩ መስቀልየ በዲበ መስቀል" እየተባልን ነው። #መድኃኔዓለም በዕለተ ዓርብ ከቀኔ በዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በገዛ ሥልጣኑ ከለየ በኋላ በኋላ ከመስቀሉ አውርደው ቀበሩት ፡፡ በ፫ኛው ቀን ሲነሣ ተሰቅሎ የነበረው የእንጨት መስቀል ሌት ተቀን በሙሉ ሳያቋርጥ እንደፀሐይ ሲያበራ በተጨማሪም አጋንንት ሲያባርር ድውይ ሲፈውስ ሙት ሲያነሣ ቤተ እሥራኤል አይሁድ ቀንተው በዓዋጅ ትልቅ ጉድጓድ ቆፍረው በመቅበር የቤት ጥራጊና አመድ ጠቅላላ የቆሻሻ መከማቻ እንዲሆን ወሰኑ፡፡

ከዚያ ዘመን ጀመሮ እስከ ሦስት መቶ ዘመን ድረስ የተከማቸው ቆሻሻ እንደተራራ ሆነ፡፡ ከዚያ በኋላ የታላቁ ቆስጠንጢኖስ እናት እሌኒ ንግሥት የተባለች ደግ ሴት የክርስቶስን መስቀል መስከረም ፲፯ ቀን ፫፻፳ ዓ.ም. ላይ በዕጣን ጢስ ምልክት ቁፋሮ አስጀምራ መጋቢት ፲ ቀን አግኝታ በማውጣት ታላቅ ቤተ መቅደስ ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር አስቀመጠችው ። ይህ መስቀልም ከዚያ ዘመን ጀምሮ እንደ ፀሐይ እያበራ ድውይ እየፈወሰ አጋንንት እያባረረ ልዩ ልዩ ተአምራትን እየሠራ ሙት እያነሳ ዕውር እያበራ ተአምራቱን ቀጠለ፡፡ ይህንንም ከኃያላን ነገሥታት መካከል የፋርስ ንጉሥ መስቀሉን ማርኮ ፋርስ ወስዶ አስቀመጠው። በዚህ ጊዜ የኢየሩሳሌም ምዕመናን የሮማውን ንጉሥ ሕርቃልን ዕርዳታ በመጠየቅ እንዲመለስ አድርገው በኢየሩሳሌም ብዙ ዘመን ሲኖር እንደገና ኃያላን ነገሥታት ይህን መስቀል እኔ እወስድ እኔእወስድ እያሉ ጠብ ፈጠሩ። በዚህ ጊዜ የኢየሩሳሌም፤የቁስጥንጥንያ፤የአንጾኪያ፤የኤፌሶን፤የአርማንያ ፤ የግሪክ ፤ የእስክንድርያ የመሳሰሉት የሃይማኖት መሪዎች ጠቡን አበረዱት ከዚህም አያይዘው በኢየሩሳሌም የሚገኘውን የክርስቶስ መስቀል ከ፬ ከፍለው በዕጣ አድርገው በስምምነት ተካፍለው ከሌሎቹ ታሪካዊ ንዋያት ጋር በየሀገራቸው ወስደው በክብር አስቀመጡት፡፡ የቀኝ ክንፉ የደረሰው ለአፍሪቃ ስለነበር ከታሪካዊ ንዋያተ ቅድሳት ጋር በግብጽ የሚገኘው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ተረክቦ ወስዶ በክብር አስቀመጠው፡፡ ይህ ግማደ መስቀልም ለብዙ ዘመን በእስክንድርያ ሲኖር በግብጽ ያሉ እስላሞች እየበዙ ኃይላቸው እየጠነከረ ሄደ። በእስክንድርያ የሚኖሩትን ክርስቲያኖች ሥቃይ ያጸኑባቸው ጀመር ክርስቲያኖቹም አንድ ሆነው መክረው ለኢትዮጵያዊ ዓፄ ዳዊት እንዲህ የሚል መልዕክት ላኩ “ንጉሥ ሆይ! በዚህ በግብጽ ያሉ እስላሞች መከራ አጽንተውብናልና ኃይልህን አንሥተህ አስታግሥልን ብለው ጠየቁት” ። ዳግማዊ ዓፄ ዳዊትም ለመንፈሳዊ ኃይማኖት ቀንተው የክርስቶስ ፍቅር አስገድዶአቸው ፳ ሽህ ሠራዊት አስከትለው ወደ ግብፅ ዘመቱ በዚህ ጊዜ በግብፅ ያሉ ኃያላን ፈሩ ተሸበሩ ንጉሡ ዳግማዊ ዳዊትም እንዲህ የሚል መልዕክት ለእስላሞች ላኩ። በተፈጥሮ ወንድሞቻችሁ ከሆኑት ክርስቲያኖች ጋር ካልታረቃችሁ ሀገራችሁን መጥቼ አጠፋዋለሁ የሕይወታችሁ መሠረት የሆነውንም የዓባይን ወንዝ ገድቤ በርሃብ ነው የምፈጃችሁ የሚል ማስጠንቀቂያ ላኩ ፡፡

የንጉሡ መልዕክት ለእስላሞች እንደደረሳቸው ፈርተው እንደጥንቱ በየሃይማኖታቸው ፀንተው በሰላም እንዲኖሩ ከክርስቲያን ወንድሞቻቸው ጋር ታረቁ፡፡መታረቃቸውን ዳግማዊ ዳዊት ሰሙ በዚህም ጉዳይ ንጉሡ በጣም ደስ አላቸው እግዚአብሔርንም አመሰገኑ የዓባይንም ወንዝ እንደ ቀድሞ ለቀቁላቸው በግብፅ የሚኖሩ ክርስቲያኖችም ከ፲፪ ሺህ ወቄት ወርቅ ጋር ደስታቸውን ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ ለዳግማዊ ዳዊት በደብዳቤ አድርገው ላኩላቸው ንጉሡም የደስታውን ደብዳቤ ተመልከተው ደስ ኣላቸው። ወርቁን ግን መልሰው በመላክ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ፃፉ በግብፅ የምትኖሩ የክርስቶስ ተከታዮች ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ የላካችሁልኝን ፲፪ ሺህ ወቄት ወርቅ መልሼ ልኬላችኋለሁ የእኔ ዓላማ ወርቅ ፍለጋ አይደለም። የክርስቶስ ፍቅር አስገድዶኝ በተቻለኝ ችግራችሁን ሁሉ አስወገድኩላችሁ አሁንም የምለምናችሁ በሀገሬ በኢትዮጵያ ረሀብና ቸነፈር ድርቅ ስለወረደብኝ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎበት የነበረውን መስቀልና የቅዱሳንን አፅም ከሌሎች ክቡራን ዕቃዎች ጋር እንድትልኩልኝ ነው የሚል ነበር፡፡ በእስክንድርያም ያሉ ምእመናን ይህ መልዕክት እንደደረሳቸው ከሊቃነ ጳጳሳቱና ከኤጲስ ቆጶሳቱ ጋር ውይይት በማድረግ ይህ ንጉሥ ታላቅ ክርስቲያን ነው፡፡ ስለዚህ ልቡን ደስ እንዲለው የፈለገውን የጌታችንን ግማደ መስቀል ከቅዱሳን አጽምና ንዋየ ቅድሳት ጋር አሁን በመለሰው ፲፪ ወቄት ወርቅ የብርና የንሐስ የመዳብና የወርቅ ሣጥን አዘጋጅተን እንላክለት ብለው ተስማምተው በክብር በሥነ ሥርዓት በሠረገላና በግመል አስጭነው ስናር ድረስ አምጥተው አስረከቧቸው። በጊዜውም በእጃቸው እያጨበጨቡ በእግራቸው እያሸበሸቡ በግንባራቸው እየሰገዱ በክብር በደስታ ተቀበሉት ይህም የሆነው መስከረም ፳፩ ቀን ነው፡፡ በኢትዮጵያም ታለቅ ብርሃን ሌት ተቀን ፫ ቀን ሙሉ ሲበራ ሰነበተ፡፡ ነገር ግን ግማደ መስቀሉ ወደ መካከለኛው ኢትዮጵያ ሳይደርስ በድንገት ዓፄ ዳዊት ስናር ላይ አረፉ፡፡ ግማደ መስቀሉም የግድ በዚያው በስናር መቆየት አስፈለገው፡፡

ከዚህ በኋላ የሟቹ የዳግማዊ ዳዊት ልጅ ዘርአ ያዕቆብ እንደነገሡ ወደ ሥናር ሔደው ግማደ መስቀሉን ከሌሎቹ ንዋያተ ቅድሳት ጋር አምጥተው በመናገሻ ከተማቸው በደብረ ብርሃን ላይ ቤተ መቅደስ ሠርተው ለማስቀመጥ ሲደክሙ ።በሕልማቸው አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል ወዳጄ ዘርአ ያዕቆብ ሆይ መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ የሚል ሕልም አዩ ፡፡ ንጉሡም መስቀለኛ ቦታ እየፈለጉ በኢትዮጵያ አውራጃዎች ሁሉ መስቀለኛ ቦታ በመፈለግ ከብዙ ቦታ ላይ አስቀምጠውት ነበር ። ለምሳሌ በሸዋ በደርሄ ማርያም ፤ በመናገሻ ማርያም ፤ በወጨጫ መስቀሉን አሳርፈውት ነበር፡፡ ነገር ግን የመጨረሻውን ቦታ ያላገኙ በመሆኑ በራዕይ እየደጋገገመ መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ እያለ ይነግራቸው ነበር፡፡ዓፄ ዘርአያዕቆብም ለ፯ ቀናት ያህል ሱባዔ ገቡ በዚያም የተገለፀላቸው መስቀልኛውን ቦታ የሚመራህ ዓምድ ብርሃን ይመጣል አላቸው እርሳቸው ከዚያ እንደወጡ መስቀለኛውን ቦታ የሚመራ ዓምደ ብርሃን ከፊታቸው መጥቶ ቆመ በዚያ መሪነት ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ ውስጥ ግሸን ከምትባል መርቶ አደረሳቸው ፡፡ ይህች ግሽን የተባለች አምባ ጥበበኛ ሰው እንደቀረፃት የተዋበች መስቀልኛ ቦታ ሁና ስለአገኟት የልባቸው ስለደረሰ ደስ አላቸው ፡፡ በዚያችም አምባ ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው መስቀሉንና ሌሎች ንዋያተ ቅድሳቱን በየማዕረጋቸው የክብር ቦታ መድበው አስቀመጧቸው ዘመኑም በ፲፬ ኛው ክፍለ ዘመን ነው፡፡ በመጀመሪያም ይህ ግማደ መስቀል ከእስክንድርያ ስናር የገባው መ
#እንግዲህ ከዓለም ጫጫታ ርቀን በእናቶች ሳምንት ብፅዕት እናታችንን እንዳናስብ ብዙሁን ዘበዘቡን አደከሙንም! #ስለዚህ ይህን እል ዘንድ ግድ ሆነብኝ ።

አደባባዮ እራሱኮ የመስቀል ቅርጽ እንጂ የጨረቃና የኮከብ ቅርጾ የለውም ቢያንስ እርሱን እንኳን ለምን አይሰሙትም ?

ጨረቃና ከዋክብት እንኳ በስቅለቱ ወቅት ካንተ በላይ ሆነን ልንታይ አይገባንም ሲሉ ከሰማይ ወደ ምድር የረገፋ አይደለምን? አንዳንዴ ከመገለጫዎቻችን ካልተማርን ሳይገባን ነው ማለት ነው ምልክታችን አርገናቸው እንደ ቁራ የምንጮኸው።

#እንደው ድከሙ ሲላቸው እንጂ አብዛኛው የሀገራችን አደባባዮች ባለ መስቀል ናቸው። መስቀል የአደባባይ አደባባይም የመስቀል ነው! አደባባዮ ብዙ ዓይነት መፈክር እና ጥቅስ የተጠቀሰበት አደባባይ ቢሆንም ቅሉ ለእንዲህ ዐይነቶቹ ግን ይህ ይላቸዋል። "ዓለም በእኔ ዘንድ የተሰቀለ ነው እኔም በዓለም ዘንድ የተሰቀልኩኝ(የተመሳቀልኩ ፣መስቀለኛ የሆንኩ) ነኝ!

#ጥያቄያችሁ እንስገድበት ሳይሆን እንስገድለት ከሆነ እናፍጥርበት ሳይሆን መስቀሉን እናፍቅርበት ከሆነ ትድኑ ዘንድ በቀንም አምስት ጊዜ ከመታጠብ ታርፉ ዘንድ አምናችሁ አንዴ ተጠመቁ ያኔ እንተዋችዋለን።
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም