ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#የነገረ_ማርያም ጥያቄዎች ምላሾች

#እውነት ወይም ሐሰት በሉ

#ኛ ማርያም ማለት እመ ብዙሐን ማለት ሲሆን በዕብራይስጥ ማሪያም በአርብኛ መሪሃም ተብላ ትጠራለች::

ሀ) እውነት ለ ) ሐሰት

#ኛ #ማርያም የሚለው ስም #አብርሃም ከሚለው ስም ጋር ከጾታ ልዮነት ባሻገር በትርጉም ደረጃ አንድ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

#ማርያም ማለት:- እመ ብዙኃን ፣የብዙኃን እናት ማለት ነው

#አብርሃም:- ማለት አበ ብዙኃን፣ የብዙኃን አባት ማለት ነው

#ኛ የኤልሳ ማሰሮ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

የኤልሳ ማሰሮ በውስጧ አጣፋጭ ጨው ተገኝቶባታል ከእመቤታችንም እናንተ የዓለም ጨው ናችሁ ብሎ ማጣፈጥን ለቅዱሳን የሰጠ የአዳምንም ሕይወት በከበረ ሞቱ ያጣፈጠ የአማናዊው #ጨው የክርስቶስ መገኛ ሆናለችና የኤልሳ ማሰሮ #የእመቤታችን ምሳሌዋ ነች

#ኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሰው ዘር ስለሆነች ጥንተ አብሶ ወይም የመጀመሪያ በደል ነክቷታል::

ሀ) እውነት ለ)ሐሰት
ምንም እንኳን እመቤታችን የሰው ዘር ብትሆንም በመንፈስ ቅዱስ ልዮ ጠብቆት ከጥንተ አብሶ(ከመጀመሪያው በደል) የነጻች ሆናለች::ወርቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው ::ወርቅ መገኛው ከመሬት ከጭቃ ውስጥ ነው ከጭቃ መገኘቱ ግን ወርቅነቱን አያስቀረውም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከተነከሩ ሰዎች የተገኘች የሰው ፍጡር ብትሆንም ነገር ግን ጭቃው ያላቆሸሻት #ንጹዑ_ወርቅ ነችና ጥንተ አብሶ የለባትም፣ አልነካትም::

#ኛ_በመዝሙር 86 ላይ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ተብሎ የተነረው ለእመቤታችን ቀደምት አያቶቿ ነው::

ሀ) እውነት ለ) ሐሰት

መጻሕፍትን ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ እንደተባለው ይህንንም ኀሠይለ ቃል አጣመው በወንድ አንቀጽ ቢቀይሩትም እንደ ጥንቱ መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው ነው የሚለው ::ይህም ሰሸለ እመቤታችን ቅደምት አያቶች ከፍታና ቅድስና የሚናገር አንቀጽ ነው ::


#ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ብቻ ምረጡ

#ኛ_ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 44÷ ከቁር 1 እስከ ያለው ኃይለ ቃል ምን ምን ነገሮችን ያስረዳል
ሀ )የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና
ለ)እመቤታችንን የወለደችሁ ቀዳሚ ተከታይ የሌለውን የአብን አንድያ ልጅ ወልድ እግዚአብሔርን ብቻ እንደሆነ::

ሐ) ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ ልጅ ዳግመኛ እንዳልወለደች

መ)ሁሉም

#ኛ_ከእመቤታችን የዘር ሐረግ ውስጥ የማይካተተው ነገድ የቱ ነው

ሀ) ነገደ ሌዊ
ለ) ነገደ ይሁዳ
ሐ) ነገደ ዳን
መ) ሀ ና ለ

#ኛ_ድንግል በድንግልና ፀንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየው ነቢይ ማን ነው

ሀ) ነብዮ ሳሙኤል
ለ)ነብዮ ኤርምያስ
ሐ)ነብዮ ኢሳይያስ
መ)ነብዮ ሐጌ

፱ እመቤታችን ለዮሴፍ የታጨችበት ምክንያት ምን ነበር

ሀ) ከውግረት እድትድን
ለ) ለጋብቻ
ሐ) ለጠባቂነት እና ለአገልጋይነት
መ) ከ "ለ" በስተቀር ሁሉም መልስ ነው


#ኛ_ እመቤታችን በቤተ መቅደስ የኖረችው ለስንት ዓመታት ነው

ሀ) ፲ ፪ ዓመታት
ለ) ፫ ዓመት ከ፫ ወር
ሐ) ለ፫ ዓመታት
መ)ለ፲ ፭ ዓመታት


#በአጭሩ_መልሱ

፲ ፩ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ድኅነት ያበረከተችሁን ትልቅ አስተዋጽኦ አብራራ(ሪ)

#መልስ

#ንጽሕናዋን ጠብቃ በመገኘቷ

#ፍቃዶን ስትጠየቅ እሺ ብላ ለድኅነተ ዓለም ምክንያት በመሆነኗ



፲ ፪ #_ድንግል ማርያም በሦስት መሠረታዊ ነገሮች ንጽዕት ነች ::እነዚህ ሦስቱ መሠረታዊ ንጽዕናዋ የምን የምን ንጽዕና ናቸው በአጭሩ ይብራራ(ሪ)

#በሥጋዋ (ንጽ ሥጋ )
#በነፍሷ (ንጽኃ ነፍስ )
#በሀሳቧ ( ንጽኃ ልቡና )

፲ ፫ #እመቤታችን " እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትሁልድ ሁሉ ብጽህይት ይሉኛል" ሉቃ 1÷49 ብላ የተናገረችሁ ስለምንድነው? ትውልዱ #ሁሉ ያለችውስ የትኛውን ትውልድ ነው

#ይህን የለችሁ
👉ነቢይት ሰለሆነች የወደፊቱን የማወቅ ፀጋ ስላላት እና በተሰጣት ፀጋ እንደ ሰጣት እንደ ፈጣሪዋ አዋቂ ስለሆነች

ትሁልድ ሁሉ ያለችው ደግሞ አማኝ ትውልድ ሁሉ ማለቷ ሲሆን በመጨረሻ ግን ክብሯ ሲገለጥ ሁሉም ትውልድ እንደሚያመሰግናት አውቃ ይህን አለች

፲ ፬ #_እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድማ ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በፊት በአምላክ ዕሊና ታስባ ትኖር እንደነበር በትምህርቱ መሠረት ቅዱሳት መጻሕፍትን እያመሳከርክ አስረዳ (ጂ)

#መልስ
."እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ እሊና ታስባ ትኖር ነቀር::፡ ለዚህመሸ "ያልተሰራ አካሌን አይኖችህ አዩኝ ፡ የተፈጠሩ ቀኖቸ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመፅሐፍ ተፃፈ" መዝ 138:16
ስለዚህ ዓለም ሳይፈጠር ሁሉም ከተፃፈ እመቤታችንም ተፅፋ ታስባለች ማለት ነው፡፡፡ቅዱሳን ነቢያት(ኤርምያስንና መጥምቁ ዮሐንስን ) ብንመለከት አሰቀድሞ ስለሚያውቃቸው መስክሮላቸዋል፡፡
" በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። " (ኤር1:5)
ስለዚህ የሁሉ አዋቂ ጌታ እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰው መሆኑ ከታወቀና ከታሰበ እመቤታችን መታሰብዋን አይዘነጋም፡፡፡
"፤ #ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4) "፤ ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1: 4)

#15.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም "ጽዮን" ተብላ የምትጠራበት የመ/ቅዱስ ጥቅስ፡

"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"
(መዝ 87:5)
" የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ፤ የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። "
(ኢሳ60:14)
" ለጽዮን ታዳጊ ይመጣል፥ በያዕቆብም ዘንድ ከኃጢአት ለሚርቁ፥ ይላል እግዚአብሔር። "
(ኢሳ59:20

#በመልሶቹ ዙሪያ ሀሳብ አስተያየት ካላችሁ
👇👇👇👇👇👇👇
@YeawedMeherte
@YeawedMeherte
ላይ ይላኩልን ::

#መልካም_ዕድል
🙏🙏🙏🙏🙏
@AwediMeherit
@AwediMeherit
Audio
#ነገረ ማርያም
#ምዕራፍ ሁለት ክፍል አምስት

#ወንድማችን #አቤኔዘር

#ይዘት
#የእመቤታችን ትንሳኤ እና እርገት ማረጋገጫዎች
#የእመቤታችን ቃልኪዳን

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#ኑ_ይህን_ድንቅ_እዩ !
______________

#የእመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ"፭ ቀናት ያክል የመገለጥ በዓል


#ከቅዱሳን_ክብር_የማርያም_ክብር_ይበልጣል ፤ የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማሕፀንዋ ተሸከመችው። ይህች ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች ከሦስቱ አካል ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና። የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት።
#ለቅዱሳን_ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት። በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሁኗልና።

#ኑ_ይህንድንቅ_እዩ። ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፤ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፤ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት።

የማይታወቅ ተገለጠ፤ የማይታይ ታየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በርግጥ ሰው ሆነ። ትላንት የነበረው ዛሬም ያለው መቼም የሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባሕርይ ነው። #ቅድስት_ሆይ_ለምኝልን


____ሶሪያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_የረቡዕ ውዳሴ ማርያም____
#ሞት_በጥር_ነሐሴ_መቃብር

መቼም ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከመሬት የሚቀር የለም :: ሞትን ሳይቀምሱ በሥጋ የተሰወሩ ቅዱሳን ሰዎች ቢኖሩም በመጨረሻ ግን የሞትን ጽዋ መጠጣታቸው ግድ ነው ሞት ወደ ክርስቶስ መሄጃ መንገድ መሸጋገሪያ ድልድይ ነውና:: ለዚህ ነው ሐዋርያው "፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ " ያለው #ፊል ፩ ÷ ፳፫
#የዛሬን አያድርገውና ሞት እንዲ ተዋርዶ እና ዝቅ ብሎ መንገድ ተብሎ እንደ ተራ ከመጠራቱ በፊት እጅግ አስፈሪ ነበር :: ሰዎች መልካምም ይሁኑ እኩያት በሞት ተግዘው ሲዖል ወስዶ መማቀቃቸው አይቀርም ነበር "፤ ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል #ኢሳ ፷ ፬ ÷፮ እንዲል ነብዮ ::
በኋላ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህች ምድር መምጣት ሞት የቀደመ መፈራቱን አጣ በትንሳኤ ተደመሰሰ በዚህም አስቀድመው እንኳንስ በደላችን ጽድቃችን እንኳ ሳይቀር እንደ
መርገም ጨርቅ ተቆጠረብን እንዳላሉ "፤ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? " እያሉ የሞትን ኃይል አቃለሉት #፩ቆሮ ፲፭÷፶፭
#ሞት በራሱ ምንም ያልሆነ የልደት ተቃራኒ ነው ነገር ግን በግብሩ ሞት ተብሎ የሚጠራው ዲያቢሎስ ነው:: ሞት የሁሉ ገዥ ሆኖ ሰልጥኟል የክብር ባለቤት መድኃን ዓለም ክርስቶስ ሳይቀር በፈቃዱ ሞትን ቀምሷል :: ይህም ከመላእክት እንኳ በጥቂቱ አነሰ ተብሎ እንዲነገርለት አድርጓል ሞት ሁሉን እንዲገዛ ያሰለጠነው እርሱ እራሱ ነው። ቢሆንም ግን ቅሉ ክብር ይግባውና ከሞት ያንሳል አያሰኘውም::

#መጻሕፍትም ይህን ግልጽ ሲያደርጉልን እንዲ ብለዋል "፤ የኃለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ
ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው። " #፩ቆሮ ፲፭ ÷፳፯ ሞት ለፈጣሪ ዓለማት ብቻም ሳይሆን ለእናቱ ለምክንያተ ድኅይን ለምትባል ለእመቤታችን ለማርያምም አልተመለሰም ::

#እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በምድር ላይ ስልሳ አራት ዓመታትን ቆይታለች ማለትም ከእናት ከአባቷ ቤት ሦስት ዓመት ከሰባት ወር፣ በቤተመቅደስ ፲፪ ዓመት፣ በቤተ ዮሴፍ ፴፬ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን እርገት በኋላ ከወንጌላዊው ዮሐንስ ጋር ፲፬ ዓመት ኖራለች፡፡ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን
አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት።

ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። እውነት ነው ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ይህ ነገረ ሞቷን &ሞትሰ ለመዋቲ
ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤( ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም
ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል ) ሲል አድንቋል ከዛም በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት።

#እሊህን_ከማርክልኝስ ይሁን አንድ ጊዜ
አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት። "ሞትኪሰ ማርያም ይመስል ከብካበ" የማርያምስ ሞት ሠርግን ይመስላል እንዲሉ አበው የእመቤታችን እረፍት እንባ መራጨት፣ ጠጉር መንጨት፣ ደረት መድቃት እንዳለበት የሰው ሞት አልነበረም፡፡ ይልቁንም አንደ ሠርግ ቤት መላዕክት
በውዳሴ፤ በማህሌት፣ በዝማሬ፣ በምስጋና ወደ ሰማይ ሸኟት እንጂ ቅዱስ ያሬድም "ተለዐለት እምድር ወበህየ ነበረት ዘምስለ ወልዳ በየማነ አብ ወመንፈስ ቅዱስ" እመቤታችን ድንግል ማርያም ከምድር ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ አለች፡፡
በዚያም ከልጇ ጋር በአብና በመንፈስ ቅዱስ ቀኝ ተቀመጠች በማለትም ዘምሯል፡፡ "፤የቅዱሳኑ ሞት
በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።" መዝ ፻፲፮ (፻፲፯) ÷፲፭ አስቀድመው ሐዋርያት ሥጋዋን በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ ብዙ ተግዳሮት ገጥሞቸው ነበር:: አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን? ኑ በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ።
#ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት። ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ
ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሦስተኛው ቀን ማክሰኞ “ #ከመ_ትንሣኤ_ወልዳ ” እንደ ልጇ ባለ ትንሣኤ ተነሥታለች።
ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከሀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ እመቤታችንም አይዞህ
አትዘን እሊያ ትንሳኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ? አላቸው አግኝተን ቀበርናት አሉት #ሞት_በጥር_በነሐሴ_መቃብር ተው ይህ ነገርስ
አይመስለኝም አላቸው ። ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብዬ እንጅ #እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው ለበረከትም ተካፍለውታል።
#በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ፲፮ ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር አድርጎ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን ዘይትራድኦ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ፍቅሯን በልቡናችን ጣዕሟን
በአንደበታችን ያትምልን
......... #ይቆየን .........
#የእመቤታችን_አማላጅነት_የልጇም_ይቅርታና_ቸርነት_አይለየን አሜን!

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ጥር ፳፩ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም
ዐውደ ምሕረት
Photo
#የመቅደሱ_ፈተናዎች
ፈተና በዓለም ሲገጥም በመቅደሱ ጥላ ተጠልሎ ፣ቆይቶ ፣ደጅ ተጠንቶ የጊዜው ጊዜ
ይታለፋል ። ግን በቤተ መቅደሱ ስንፈተን ወዴት ሄደን ፈተናውን ማለፍ ይቻለን ይሆን!?።
ከባድ ነው !“ መዝ 39(40)፥1
#እመ_አምላክ_ቅድስት_ድንግል_ማርያምን የገጠማት ከባዱ ፈተና ይህው የመቅደሱ
ፈተና ነበር።
ክቡራን የሆኑ ወላጆቿ ቅድስት ሐናና ቅዱስ እያቄም እግዚአብሔር የዓይናችን ማረፊያ
የልባችን ተስፈ የምትሆን ልጅ ቢሰጠን ውኃ ቀድታ ጥጥ ፈትላ ታገልግለን አንልም በቤትህ
የምታገለግል አድርገን ላንተው እንሰጣለን እንጂ ሲሉ በተሳሉት ስእለት መሠረት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ነሐሴ ሰባት ቀን ጸንሰው ግንቦት አንድ ቀን ወለዷት

ሦስት ዓመት ሲሆናትም ቅድስ ሐና በስእለታችን መሠረት ለእግዚአብሔር ልንሰጣት
ያስፈልገናል ይዘናት ወደ ቤተ መቅደስ እንሂድ አለች ቅዱስ እያቄምም የልጅ ፍቅርሽ
ይውጣልሽ ብዬ እንጂ ዝም ያልኩት ነገሩንስ ሳስበው ነበር ካንቺ ከመጣማ በይ ነኝ
ስእለታችንን እንፈጽም አለ። “ሰነፎች ደስ አያሰኙትምና ለእግዚአብሔር ስእለት በተሳልህ
ጊዜ ትፈጽመው ዘንድ አትዘግይ፤ የተሳልኸውን ፈጽመው።” ተብሎ ተጽፎልና መክብብ 5፥4
# ወደ_ቤተ_መቅደስ ሲደርሱ የመጀመሪያው ፈተና መጣ በቤተ መቅደስ መኖሯስ ጥሩ ነገር
ነበር ግን የምግቧ ነገር እንዴት ይሆናል? የሚል ፈተና። ብዙቹ የቤተ መቅደሱ መተናዎች
ይህ እኮ ጥሩ ነበር ብለው የሚጀምሩ ሲሆኑ እመካከላቸው ግን የሚል አፍራሽ ቃል ወይም
ድርጊት የተቀላቀለበት ነው። ቄስ እገሌኮ ሲቀድሱ ድምጣቸው ውብ ነው ግን ሰዓት
ያስረዝማሉ ፤ ሰባኪ እንትና አቤት ትምህር አሰጣጡ ግን ትንታኔ ያበዛል ፤ ዘማሪማ እንደ
እሷ ያለ የትም አይገኝም ግን ወደ ዘፈን ትወስደዋለች ። ግን...ግን... ግን...
" #አሁን_ከሰማይ የወረድኩ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" የሚል የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን
የምትወልድ ሆና ሳለ ቁራሽ እንጀራ አጡላትና በመቅደስ መኖሯ ጥሩ ነበር ግን ምን ትበላ
ይሆን ? ብለው ተቸገሩ ዮሐ 6÷56 የብትውና ሕይወት ከሰዎችና ከዓለም ምኞት
የሚገለሉበትና የሚርቁበት ሕይወት እንጂ ከፈተና የሚገለሉበት ሕይወት አይደለም ይልቁኑ
ፈተና በብቸኞች (ባዕታዊያን)ላይ ይበረታል። በዐታዊቷ እመቤታችንም ወደ በዓቷ ከመግባቷ
እስከ መውጧታ በአያሌው ተፈትናለች።
ዲያቢሎስ ተንኮለኛ ነው አስቀድሞ በመቅደስ የሕይወት ፍሬ መገኛ የሆነች ጸዋሪተ ፍሬ
ኤፍራታን እመቤታችንን ምግብ የሌለ አስመሰሎ በእጅጉ ፈተናት በኋላ ልጇ ወዳጇን ኢየሱስ
ክርስቶስን ደግሞ በመቅደሱ በገዳመ ቆሮንቶስ ተገናኝቶ ድንጋዮን ዳቦ አርግና እንብላ እያለ
በምግብ መትረፍረፍ ይፈትን ዘንድ አለውና " በዘርህና በዘሯ መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ
እንደተባለ" ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን በመቅደሱ በገዳመ ቆሮንቶስ የገጠመውን የስስት
ፈተና በትእግሥት ድል የሚነሳው ነው እናቱ እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያምም ይህን የመቅደስ ፈተና በቅዱስ ፋኑኤል እጅ በሚታይ በሰማያዊ መና
በተትረፈረፈ በረከት ድል የነሳችው ሆነች ።
#ሌላኛው_የመቅደስ ፈተና በቤተ መቅደሱ ጸንተን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሥራ
ሊሰራብን ባሰበ ጊዜ የሚገጥም የፈተና አይነት ነው 12 ዓመት በቤተ መቅደት ተቀምጣ
15ዓመት በሆናት ጊዜ መላእኩ ተልኩ መጥቶ ደስ ያለሽ ደስተኛይቱ ሆን ከሦስቱ አካላት
አንዱን አካል ከሦስቱ ቅዱስ አንዱን ቅዱስ ያለ ዘርዓ ብሕሲ (ያለ ወንድ ዘር) ትጸንሺዋለሽ
ትወልጅማለሽ ስሙንም አማኑኤል ትይዋሽ ብሎ አበሰራት ይህ ጊዜ አይሁድ ሴት ያለ ጋብቻ
ጸንሳ ከተገኘች በድንጋይ ተወግራ ትሙት የሚል ሕግ ነበራቸውና እንዳይወግሯት ጻድቁ
ዮሴፍ ይጠብቃት ዘንድ ተመረጠ አይሁድ ግን ቤተ መቅደሳችንን ታረክሳለች እንዴት ያለ
ወንድ ልትጸንስ ትችላለች አሉና ማየ ዘለፋ የተጸነሰ ጽንስ የሚያሶርድ መጠጥ ሰጧት
ጠጥታ የምትሞት መስሏቸው ቢያዮ ጨራሽ ፊቷ ከፀሐይ ሰባት እጅ አበራ በዚህ
ትተዋታል።
ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኃላ በስምተኛው ቀን ሌላኛው የመቅደሱ ፈተና መጣ
ይገርዙት ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ሄዱ የማዳኑን ነገር ሳያይ እንዳይሞት ተስፋ
የተሰጠው ስምዖንን በቤተ መቅደስ አገኙትና ባረካቸው እንዲም አለ " ጌታ ሆይ፥ አሁን
እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን
ማዳንህን አይተዋልና፤ ........እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል
ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥
በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት።” ሉቃስ 2፥29-35 የስእለትም ልጅ
አይደለች መከራዋ ብዙ ነውና ። እረፍት ያጣች እርሷ የብዙ ደካሞች እረፍታችን ሆነች
መከረኛዋ እርሷ የመከረኞች ተስፋችን ሆነች ። በበዐቷ የተፈተነች ብቸኞች እኛኝ ከፈጣሪና
ከአእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጋር አዛመደችን።
#የእመቤታችን_የቅድስት_ድንግል_ማርያም እረድኤትና በረከት በሀገራችን በኢትዮጵያ
በሕቦቿም በሕዝበ ክርስቲያኖች ላይ ዘለለዓለሙ ጸንቶ ይኑር!አሜን!
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ታህሳስ3/2013ዓ.ም
"ዕርገተ ክርስቶስ እንደ ሃይማኖት"

#በጸሎተ ሃይማኖታችን ከምንመሰክራቸው ምስክርነቶች አንዱ "በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ" የሚል ነው።በዚህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በኋላ እንዳረገ ማመናችንን እንገልጣለን።ይህንን ሃይማኖታችንን ያገኘነውም "የእግዚአብሔር መንፈስ ካለባቸው" ቅዱሳት መጻሕፍት ነው።(2ኛ ጢሞ 3:16)

ቅዱስ ዳዊት "በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" (መዝ 67:33) ቅዱስ ሉቃስ ደግሞ "ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ" (ሉቃ 24:51) ብለውናል።እነዚህም የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነቶች ናቸው።

"ዕርገተ ክርስቶስ በነገረ ማርያም"

#የእመቤታችን ወዳጅ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ" ሲል ያመሰግናታል።ይኸውም ለቃል ርደት(መውረድ (ሰው መሆን) ) ለሥጋ ዕርገት ( ከፍ ማለት (አምላክ መሆን) )ምክንያት ድንግል ማርያም ናት ማለት ነው።ቃል ሥጋ ሲሆን ሥጋም ቃልን በመሆን ከፍ ያለው (ያረገው) በማኅፀነ ድንግል ማርያም ነው።ኋላም ከተነሣ በዐርባኛው ቀን ያረገው ከእመቤታችን ሰው በሆነበት ሥጋ ነው።በዕርገቱ ጊዜ ከእናቱ የነሣው (የተዋሐደው) ሥጋ አልተለየውም።"በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ..." በሚለው ኃይለቃል ውስጥ ያለው "ምሥራቅ" የሚለው ቃልም "ሥጋ ማርያም"ን ያሳያል።ጌታ ፀሐየ ጽድቅ ሆኖ ከእርሷ የወጣባት ምሥራቅ ድንግል ማርያም ናትና።ስለዚህ ኃይለ ቃሉ "በድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ተብሎ ይተረጎማል።

"ዕርገተ ክርስቶስ በአምልኮአችን"

#ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትገለጥበት ትልቁ አምልኮዋ ቅዳሴ ነው።የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ "አሜን" ( አሜን ለሃይማኖት ሲሆን ትክክል/እውነት ማለት ነው) እያለች ከምትናገራቸው ምስክርነቶቿ አንዱ "ነአምን ዕርገተከ ወዳግመ ምጽአተከ" (ዕርገትህን እናምናለን ሁለተኛ መምጣትህንም) የሚል ነው።እንዲሁም ካህኑ "አልዕሉ አልባቢክሙ" (ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ) በማለት ከፍ ከፍ ያለውን አምላካችንን ሲያሳስበን ዲያቆኑ ደግሞ "ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ" ብሎ የጌታን በምሥራቅ ማረግ ያስታውሰናል።ልቡናን ከፍ ከፍ ማድረግም በዓይነ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር ጌታን ሲያርግ መመልከት ፤ በዕዝነ ልቡና የቅዱሳን መላእክቱን ዝማሬ ማድመጥ፤ በአንፈ ልቡና መዓዛ ዕርገቱን ማሽተት ፤ በእግረ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር በደብረ ዘይት መቆም፤በአብራከ ልቡና ለጌታችን መስገድና በዚህ ሁሉ መደሰት ነው።"እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" እንዲል (ሉቃ 24:52)

"ዕርገተ ክርስቶስ በክርስቲያናዊ ሕይወት"

#ጌታችን ወደ ላይ ከፍ ከፍ እንዳለ ክርስትናም ከፍ ከፍ የማለት ሕይወት ነው።ተወዳጅ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ "በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል" (1ኛ ዮሐ 2:6) እንዳለ ጌታችን ከፍ ከፍ እንዳለ እኛም በቅድስና ከፍ ከፍ ልንል ይገባናል።ይህ የቅድስና ሕይወትም ከሥጋ ንጽሕና ወደ ነፍስ ንጽሕና ከነፍስ ንጽሕና ወደ ልቡና ንጽሕና የሚደረግ ጉዞ ነው።ከሁሉ አስቀድመን ግን ከስድብ ወደ ምስጋና፣ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ከቂም ወደ ይቅርታ፣ከዓለም ወደ ቤተክርስቲያን፣ከፍልስፍና ወደ ሃይማኖት፣ከገዛ አጉል እሳቤአችን ወደ እግዚአብሔር ሐሳብ ከፍ ከፍ ልንል ያስፈልገናል!!!

"ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው ፤ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን።" (2ኛ ተሰ 4:17)

መድኃኔዓለም እንዲህ ያለውን የክብር መነጠቅ በቸርነቱ ያድለን !!!

ሰኔ 07/2016 ዓ.ም

#ኢዮብ ክንፈ
#ከሕግ በላይ ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ንጽሕት ነሽ።ከአንቺ በቀር መርገመ አዳም ወሔዋን የቀረለት የለምና።
#ከሕግ በላይ ጌታን በድንግልና ፀንሰሽ በድንግልና ወለድሽ።ድንግልም እናትም ሆንሽ፤ያውም ወላዲተ አምላክ
#ከሕግም ውጪ መርገም ሳያገኝሽ ኃጢአት ሳይኖርብሽ ሞትን ቀመስሽ።ሞት የኃጢአት ውጤት ነውና!!!
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ #ለማርያም የዐፅብ ለኩሉ"
"ሞትስ ለሟች ይገባል ፤ #የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል"

#ኃጢአትን ሳይሠሩ ሞትን መቅመስ(ሞተ ሥጋም ቢሆን በቀደመው በደል የመጣ ነውና) ፤ ደግሞ ኃጢአትን ሠርቶ #በእመቤታችን የዕረፍት ቃልኪዳን ተማምኖ ዝክር አድርጎ ከዳግም ሞት መዳን!!!
#የእግዚአብሔር ፍርዱ ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!

#የእመቤታችን በረከቷ ይደርብን፤ፍቅሯ አይለየን!!!

#አስተርእዮ #ማርያም / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ዛሬ የኪዳናት ሁሉ ፍጻሜ #ኪዳነ #ምሕረት ናት።ለቅዱሳኑ ለአዳም፣ለኖኅ፣ለመልከጼዲቅ፣ለአብር
ሃም፣ለዳዊት የተገባው ቃልኪዳን ሁሉ በእግዝእትነ ድንግል ማርያም ፍጻሜውን አገኘ።ይህ ኪዳነ እግዚአብሔር ምንድነው? ቢሉ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆን ነው።ሰው ሆኖም መዳናችንን መፈጸም ነው።

#ቅዱስ ዳዊት “ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።” መዝ 3፥8
ብሎ እንደተናገረው ሰውን ከተፈረደበት የሞት ፍርድ ማዳን የሚቻለው የፈረደበት እግዚአብሔር ነው።

#“ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል፤ የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።”(መዝ 33፥5) በሚለው ቃልም ምን እግዚአብሔር ሰውን ማዳን(ጽድቅ) ቢችልም ፍርድንም ይወድዳል።ሰውን በቸርነቱ የማዳን ፈቃዱ ጽድቅ ሲሆን፤የበደለ ሰው ነውና ሊክስ የሚገባውም ሰው ነው፦ይህ ፍርድ ይባላል።
ሰው ደግሞ ራሱ የሞት ፍርድ ስላለበት ሰውን ማዳን የማይቻለው ነው።ታዲያ ምን ተሻለ? የሞት ፍርድ የሌለበት፤የባሕርይ ጉስቁልና (fallen nature)፤መርገመ አዳም መርገመ ሔዋን ያላገኘው ንጹሕና ቅዱስ ሰው ነዋ !!! ይህንን ነቢዩ ኢሳይያስ
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።”
(ኢሳ1፥9) በማለት የገለጸው ከላይ ካነሣናቸው ጉዳዮች የቀረች ንጹሕ ዘር ታስፈልግ ነበር።ከዚህች ንጹሕ ዘር ነው ራሱ እግዚአብሔር የነሣውን ሥጋዋን ነፍሷን ተዋሕዶ የሚያድነን።

#ይህቺ አዳምና ሔዋን በበደሉት በደል ከመጣው ጣጣ ሁሉ ከአዳም ልጆች በተለየ መልኩ ያስቀራት ዘር እመቤታችን ናት።ልብ በሉ "ዘርን ባያስቀርልን" አለ እንጂ "ዘሮችን" አላለም።ዘርዪቱ አንዲት ናት።ልዩ ናት!!!አትደገምም፤አትነገርም።ይህቺ ሰዎች ሁሉ ላይ ከመጣው የሞት ዕዳ የቀረች (የተረፈች) ዘር እመቤታችን ለመሆኗ ሰማያውያን መላእክትን ምድራውያን ጻድቃንን ምስክር እናቆማለን።“እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ።”(ኢሳ 1፥2)

1.“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
(ዘፍ 3፥15) የሰማዮች ሰማይ እግዚአብሔር የተናገረው ቃል ነው።ይህቺ ከእባቡ (ከሰይጣን) ጋር ጠላትነት ውስጥ የምትገባ ዘር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።ሔዋን ከመሰለችህ ተሳስተሃል።ስለ እርሷማ ቅዱስ ኤፍሬም "ከይሲ ዲያቢሎስ ያሳታት ሔዋንን እግዚአብሔር ምጥሽንና ፃዕርሽን አበዛዋለሁ ብሎ ፈረደባት"ብሎ ተናገረ ።በምክረ ሰይጣን የተስማማ ሰው ከሰይጣን ጋር ጠላትነት ውስጥ ሊገባም አይችልም።ይህ የእመቤታችንና የሰይጣን ጠላትነት “ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ”
(ራእይ 12፥17) ተብሎ ተጽፎለታል።ዘንዶው ማንነው? ካልክ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።”(ራእይ 12፥9) በማለት የቀደመው እባብ (ሰይጣን) መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ ይነግርሃል።ሴቲቱስ?“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”ራእይ 12፥1
የተባላለት ድንግል ማርያም ናት።በዘፍጥረት በሴቲቱና በእባቡ ጠላትነት እንደሚደረግ እግዚአብሔር ነገረን።ቅዱስ ዮሐንስ ይህን ጠላትነት በተግባራዊ መልኩ በራእዩ አስረዳን።

2. “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።”(መዝ 45፥4) ልዑል እግዚአብሔር ማደሪያውን ለየ፤አመሰገነ፤አከበረ።
ቅዱስ እግዚአብሔር ማደሪያው የምትሆን ድንግል ማርያምን ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ጠበቀ ፤ በመጠበቁም አከበረ።

3.“ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።”ሉቃ1፥27
ቅዱስ ገብርኤል የተላከው "ከደናግል ወደ አንዲቱ" አይደለም፤ወደ "አንዲት ድንግል" እንጂ!!!በሥጋ ደናግል የሆኑ ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ።እነዚህ ግን እንደ ማንኛውም የሰው ዘር መርገመ አዳም ወሔዋን ደርሶባቸዋል።እመቤታችን ግን ከዚህ ሁሉ ንጽሕት ናትና "አንዲት ድንግል" አላት።"አንዲት ድንግል" ማለትም "ብቸኛዪቱ ድንግል" ማለት ነው።ይህ ዓይነቱ ድንግልና ነው "የድንግልናሽ ምስጋናና ክብር ታላቅ ነው" ተብሎ የተመሰገነ።

4. “መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።”(ሉቃ 1፥28)
ሰው ሁሉ ኃዘን አግኝቶት "ደስ ይበልሽ" የተባለች፤ሰው ሁሉ ከጸጋ እግዚአብሔር ጎድሎ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" ተብላ የተመሰገነች፤በበደል በደሉንም ተከትሎ በደረሰብን መርገም ከእግዚአብሔር ተለይተን በነበርን ጊዜ መርገምም ሆነ በደል ካላገኛት ከእመቤታችን ጋር ጌታ እግዚአብሔር ነበር።ከሌሎች ሴቶች መካከል የተባረከች ናት እመቤታችን።መባረክ የመረገም ተቃራኒ መሆኑ ግልጥ ነው።ሌሎች ሴቶች ላይ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።” (ዘፍ 3፥16) የተባለው መርገም ሲደርስባቸው በእመቤታችን ግን ይህ ሁሉ የለባትም።

#በእውኑ #የእመቤታችን ሥጋ የወደቀው የአዳም ሥጋ እንዳልሆነ፤አዳም ሳይበድል የነበረው ሥጋ እንደሆነ ዐወቅን ተረዳን!!!ይህንን የገለጠልን ለእመቤታችን የምሕረት ቃል ኪዳን የሰጠ ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!

#የካቲት #ኪዳነ #ምሕረት /2017 ዓ.ም

#ኢዮብ ክንፈ