ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
930 photos
24 videos
271 files
193 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#አማኑኤል:- #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ!

"ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።” #ዮሐ ፩ ፥ ፲ ፬
#ቸሩ ሆይ ቸሩ ሆይ ናና
#ቸሩ ሆይ አማኑኤል ናና
#የእስራኤል መና ቸሩ ሆይ ናና
#ቸሩ ሆይ መድኃኔዓለም ናና
#ሊቀ_መዘምራን_ቀሲስ_ምንዳዬ_ብርሃኑ
#እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ
#ሉቃ ፬ ÷ ፲ ፮

ምኩራብ የአይሁድ የጸሎት ሥፍራ መጠሪያ ነው። የአይሁድ አምልኮ በኢየሩሳሌም ባለ ቤተ መቅደስ ሥርዓት የሚፈጸም ነበር ናቡ ከደነጹር ቤተ መቅደሱን ካፈረሰ እና ሕዝቡንም ካፈለሰ በኃላ ግን አይሁድ በየደረሱበት " #ምኩራብ" እየሰሩ ጸሎትና ትምህርት እንዲሁም ሌሎች የአምልኮ ሥርዓቶችን ያስቀጥሉ ጀምረዋል። አሥር የጎለመሱ ወንዶች ሲገኙ ምኩራብ መሥራት ይፈቀድላቸዋል ቤቱም ወይም ምኩራቡም ትንሽ ወይም ትልቅ ሊሆን ይችላል።/የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃል ገጽ ፷ /

#ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመንፈስ ኃይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ስለ እርሱም በዙሪያው ባለችው አገር ሁሉ ዝና ወጣ። እርሱም በምኵራባቸው ሲያስተምር፥ ሁሉም ያመሰግኑት ነበር።

ይህ ምኩራብ እየተባለ የሚጠራው የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈ ጌታ በአይሁድ ምኩራብ ገብቶ መጽሐፍ እንዲሰጡት ጠይቆ የሚሰሙት ቃል ዛሬ በጆሯቸው እንደተፈጸመ እንዲህ ሲል እንደ ነገራቸው ይዘከርበታል፦

ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ #እንደ_ልማዱም_በሰንበት_ቀን_ወደ_ምኵራብ_ገባ__ሊያነብም_ተነሣ። የነቢዩንም የኢሳይያስን መጽሐፍ ሰጡት፥ መጽሐፉንም በተረተረ ጊዜ። የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል ተብሎ የተጻፈበትን ስፍራ አገኘ። መጽሐፉንም ጠቅልሎ ለአገልጋዩ ሰጠውና
ተቀመጠ፤ በምኵራብም የነበሩት ሁሉ ትኵር ብለው ይመለከቱት ነበር። እርሱም። ዛሬ ይህ መጽሐፍ በጆሮአችሁ ተፈጸመ ይላቸው ጀመር።

#ሁሉም_ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው ቃል የተነሣ እየተደነቁም ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? ይሉ ነበር። እርሱም፦ ያለ ጥርጥር ይህን ምሳሌ። ባለ መድኃኒት ሆይ፥ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ አድርግ ትሉኛላችሁ አላቸው። #ሉቃ.፬÷፲ ፬ -፳ ፫

ሳምንቱ ምኩራብ ተብሎ የተሰየመበት ሌላው ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት « #ቦአ_ኢየሱስ_ምኩራበ_አይሁድ » «ኢየሱስ በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ» እያለ ኢየሱስ ክርስቶስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ጅራፍ ጀርፎ አንድም ከሐዋርያቱም ተቀብሎ ይላል ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች እናንተ ግን የወንበዴዎች መናህሪያ አደረጋችኋት" ብሎ እየገረፈ ከመቅደስ እዳባረራቸው ገበቴያቸውምን እንደ ገለበጠ ገብያቸውንም እንደፈታባቸው የሚሰበክበት የሚተረክበት ሳምንት ጭምር በመሆኑ ነው ፡፡ #ማቴ ፳ ፩ ፥ ፲ ፪-፲ ፫ ተጠቅሷል፡፡ “ሰንበታቴን ጠብቁ፥ መቅደሴንም ፍሩ፤ #እኔ_እግዚአብሔር ነኝ።” እንዳለ መጻሕፍ #ኦ.ዘሌ ፳ ፮ ፥ ፪.
#ጌታችን_መድኃኔታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በምድር ሲመላለስ ከዚህ ቀደም በምኩራቦቻቸው ተሰምቶ የማይታወቅ የወንጌል ትምህርት እንዳስተማራቸውና ዕውራን እንዲያዩ፤ ደንቆሮዎች እንዲሰሙ፤ ዲዳዎች እንዲናገሩ በማድረግ እንዲሁም ደግሞ ሙታንን በማሥነሳት የተለያዩ ድንቅ ተአምራቶችን በማድረግ የወንጌልን ኃይል ስለማሳየቱ ይተረክበታል።

"እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ (የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና) #መዝ ፷ ፰ ( ፷ ፱ )፥ ፱ ተብሎ እንደተጻፈ ሕገ እግዚአብሔር እንዲፈጸም፤ ሕገ ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ፤ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዳይበላሽ በአይሁድ ምኩራብ በመግባትእንዳስተማረ ሁሉ ዛሬም እያንዳንዳችን የቤተ ክርስቲያንን ነገር ለቤተ ክርስቲያን በማድረግ በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ነገርን ብቻ በመሥራት ለቤተክርስቲያ የሚገባትን ቦታ መስጠት እንደሚገባ ይስበክበታል። ይልቁኑ በአርያ ሥላሴ የተፈጠረ ሰውነታችን ምኩራብ እየተባለ ይጠራል በዚህ ሰውነት ኃጢያትን መሸጥ መለውጥ ማርከስ እንደማይገባም ልብ ሊባል ይገባል። ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። ስለዚህ አይሁድ፦ ይህ ቤተ መቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን?አሉት። #እርሱ_ግን_ስለ_ሰውነቱ_ቤተ_መቅደስ ይል ነበር። #ዮሐ ፪÷፲ ፱-፳ ፩ “ #የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ #የእግዚአብሔርም_መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ” ማንም #የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ #እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ #የእግዚአብሔር_ቤተ_መቅደስ_ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።” #፩ኛ_ቆሮንቶስ ፫ ፥ ፲ ፯

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፲ ፩/ ፳ ፻ ፲ ፫.ዓ.ም
#ልትድን ትወዳለህን?"
#ዮሐ ፭÷፮
የዐቢይ ጾም አራተኛው ሰንበት “መጻጉዕ” ይባላል፡፡ መጻጉዕ ማለት “በሽተኛ” ማለት ነው፡
በዚህ ዕለት ጌታችን በቤተ ስዳ መጻጉዕን ማዳኑን ቤተክርስቲያን ትሰብካለች፡፡ ለ ፴ ፰
ዓመታት ያህል የፈውስ ተስፈኛ ሆኖ በመጠመቂያው አጠገብ የኖረ መጻጉዕን በአልጋው
ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ ‹‹አዎን›› እንደሚለው እያወቀ
መጻጉዕን ‹‹ልትድን ትወዳለህን?” አለው።
#መጻጉዕም ‹‹ሰው የለኝም›› በማለት የመዳን ጉጉቱን ከወዳጅ አልባነቱ ጋር ገለጠ።
ጌታም ‹‹ተንስና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ” አለው፡፡ ወዲያው አፈፍ ብሎ በፍጥነት ያን ሁሉ
ዘመን የተሸከመችውን ጠንካራ አልጋ ተሸክሟት ሄደ (ዮሐ ፭÷፩ -፭)።
ጌታችን መጻጉዕን ‹‹ ተነስተህ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ›› ያለው ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡
አንደኛው ቅዱስ ኤስድሮስ እንዳለው አልጋው ጠንካራ የብረት አልጋ ነበረና ጽንዓ
ተአምራቱን ለማሳየት ነው፡፡ ሁለተኛው ‹‹ታዲያ ቢያድነኝ በከንቱ መች ሆነና የገዛ አልጋዬን
ትቼለት የመጣሁ ለመዳኔ ዋጋ የከፈልኩበት አይደለምን?›› እንዳይል መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ‹‹ያለህን ይዘህ ሂድ እኔ ከአንተ አንዳች አልሻም›› ባሰኘ ቃል ‹‹አልጋህን
ተሸክመህ ሂድ›› ብሎታል።
# ይህ_ሰንበት የሕሙማን ፈውስ መታሰቢያ ዕለት ነው። የሰንበቱም ስያሜ በዕለቱ
የሚነበቡትን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢርና የጾመ ድጓውን ይትበሀል ተከትሎ የተሰየመ
ነው፡፡ በመልእክታቱ የሚነበቡት (ገላ ፭÷፩ እና ያዕ ፭÷፡፲ ፬) ስለ ድውያን መፈወስ
የሚያወሱ ናቸው፡፡ ከሐዋርያት ሥራ የሚነበውም እንዲሁ (ሐዋ ፫÷፩)፡፡ የዕለቱ ምስባክ
እንዲሁ የድውያንን መፈወስ የሚሰብክ ሲሆን “እግዚአብሔር በደዌው አልጋ ላይ ሳለ
ይረዳዋል፤ መኝታውንም ሁሉ ከበሽታው የተነሳ ይለውጥለታል፡፡ እኔስ “አቤቱ ይቅር በለኝ፤
አንተን በድያለሁና ለነፍሴ አስተስርይላት” አልሁ፡፡” ይላል (መዝ ፴ ፱(፵)÷፫)
መጻጉዕ ማለት ድዊ፣ ሕመምተኛ፣በሽተኛ ማለት ነውና በቤተ ሳይዳ ፴ ፰ ዓመት በአልጋ
ቁራኛ በደዌ ዳኛ ተይዞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ የፈወሰው ሰው ስም ብቻ
አይደለም የዚያ ሰው ስም "ስምዖን" ነው። ሕመምተኞች ሁሉ መጻጉዕ ተብለው ሊጠሩ
ይችላሉ ።ስለሆነም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን የዐቢይ ጾም አራተኛ ሳምንት መጻጉዕ
ብላ ስታስብ ሕሙማነ ነፍስን እሙማነ ሥጋን ሁሉ ፈውሰ ነፍስ ፈውሰ ሥጋ እንዲያገኙ
ታስባቸዋለች ማለት ነው ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመዋለ ስብከቱ
እሙማነ ነፍሳትን በትምህርቱ እሙማነ ሥጋን በተአምራቱ እንደፈወሳቸውም
ታዘክርበታለች።
#ሕማማ ወይም ደዌ በ ፭ ዓይነት መንገድ ሊመጣ ይችላል። እነርሱም
፩, ደዌ ዘንጽሕ(በንጽሕና የሚመጣ በሽታ) ለአብነትም እንደ ጢሞቲዎስ በአገልግሎት
ምክንያት የሚመጡ ::እንደ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት።
፪, ደዌ ዘእሴት (ለዋጋ የሚመጣ በሽታ) እንደ ጻድቁ ኢዮብ
፫, ደዌ ዘተአምራት( የእግዚአብሔር ተአምራት እንዲገለጥ የሚመጡ በሽታዎች) እንደ
ዘውር ተወልደ
፬, ደዌ ዘመቅሰፍት(በቅጣት የሚመጣ በሽታ)
እንደ ፈርዖን ዘመን ያሉ በሽታዎችና አባር ቸነፈሮች በዘመናችን ኮረና
፭,ደዌ ዘኃጢያት (በኃጢያት ምክንያት የሚመጣ) አንደ መጻጉዕ ፣ እንደ ባለ ሽቶዋ
ማርያም፣ በድንጋይ ልትወገር እንደነበረችው አመንዝራ ሴት
#ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ድኅነትን በ፭ መንገድ ይፈጽምላቸው
ነበር።ይህውም
፩,በኃልዮ (በሀሳቡ) ማር ፩፥፳ ፭
፪,በነቢብ(በንግሩ) ማቴ፲ ፭፥፳ ፰፣ ዮሐ ፭÷፰
፫,በገሲስ(በመዳሰስ) ማቴ፰፥፫ ፣ማቴ ፰፥፩ ፭
፬,በዘፈራ ልብስ (በልሱ ዘርፍ) ሉቃስ ፰፥፵ ፬
፭,በወሪቀ ምሪቅ (ምራቅን እንትፍ በማለት)“ ዮሐ ፱፥፮
ለድኅነት የሰው በጎ ፍቃድና ፍላጎት እጅግ አስፈላጊ ነው።መጻጉን ልትድን ትወዳለህን ብሎ
የመጠየቁም ምጢር ይህ ነበር ሰው ነጻ ፍቃዱ ሊነፍገው አይሻምና ። ሰው ለመዳን ወይም
ሌላውንም ለማዳን ብርቱ ጥረትን ሊያደርግ ይገባዋል
መጽሐፍ ቅዱስ አራት ሰዎች አንድ ሕመምተኛ ለማዳን የተጠቀሙትን ብርቱ ጥረት እንዲ
በግሩም ተርኮልን እናነባለን።
" #አራት_ሰዎችም የተሸከሙትን ሽባ አመጡለት። ስለ ሕዝቡም ብዛት ወደ እርሱ ማቅረብ
ቢያቅታቸው እርሱ ያለበትን የቤቱን ጣራ አነሡ፥ ነድለውም ሽባው የተኛበትን አልጋ
አወረዱ። # ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፦ አንተ ልጅ፥
ኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው። ማር ፪ ÷፫-፭
.............ይቆየን.......
ግብሐት :-የዮሐንስ ወንጌል ም፭ ትርጓሜው
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፲ ፱ ቀን/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
" #በእናቴ ስም ጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲታነጽ ፍቃዴ ነው"
_________________________


#እመቤታች_ቅድስት_ድንግል_ማርያም እንደ ልጇ ባለ ሞት ሞታ እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ከሞት ተነስታ ባረገች በ4ዓመቷ ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ፊልጵስዮስ ገብተው አስተማሩ ሕዝቡም አምነው ተጠመቁ። ከእግዲህ ወደ ቤተ ጣዖት አትሂዱ አሏቸው የለመድነውን ከከለከላችሁንማ መካነ ጸሎት(የጸሎት ቦታ) ስጡን ፣ ሥሩልን አሏቸው።

#በእውነቱ የሚገባ ጥያቄ ነው ! አንድ ውኃ የያዘ ብርጭቆን ውኃውን ከገለበጥንለት በኋላ ባዶዎን የሚቀመጥ አይደለም ምንም እንኳ በዐይን ባናየውም በእርሱ ፋንታ ብርጭቆውን አየር ይሞላዋል። ሰውም እንዲሁ ነው ሲሰራው የነበረን አንድ ክፉ ልማድ ከሕይወቱ ሲያስወጣ በዛ ባስወጣው ቦታ ሌላ ሰናይ የሆነ ነገርን ሊተካበት ይገባል ።ካልሆነ ግን ክፉ መስራት ትቻለው ደግ ባልሰራ ችግር የለውም ብሎ ክፋትን ትቶ በጎንም ሳይሰሩ መቀመጥ አያጸድቅም " መልካም ሥራ መሥራትን እያወቀ ለማይሰራት ኃጢያት ትሆንበታለችና"


በተጨማሪም ያን ክፉሁን አስወጥቻለው ብሎ ያለ ደግ ሥራ የተቀመጠው ሰው ቤቱን ባዶ አድርጎ እንደጠረገ ሰው ይመስላል ከእርሱ የወጣ አጋንንትም በምድረ በዳ ሲዞር ቆይቶ የዚያ ሰው ቤት(ቤተ ልቡናው) በደግ ሥራ ያልተሞላ ሆኖ ሲመለከት ወደ ቀደመ ቤቴ ልመለስ ይልና ከእርሱ የከፉ ሌሎች ሰባት አጋንንትይ ይዞ ተመልሶ ይገባበታል ለሰውየውም ከድሮ ይልቅ የአሁኑ ሕይወቱ የከፋ ይሁንበታል #ማቴ 12÷45 #ሉቃ 10÷26

#የፊልጵስዮስ አማኞች ጥያቄ የተገባ ነው ያልነው ለዚሁ ነው ሰው ወደ ቤተ ጣዖት መሄዱን ሲያቆም በአንጻሩ በዚያ ፈንታ ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሄድ መጀመር አለበት አለበለዚያ ግን ከቤተ ጣዖት ከቀረው ወደ ቤተ እግዚአብሔር ባልሄድም ችግር የለውም ማለት አይገባውም እርሱ ወደ ቤተ ጣዖት መሄድ አቆመ ማለት የቤተ ጣዖቱ ሥርዓትና ልማድ በሀሳብ ሁሉ ወደ እርሱ መምጣታቸው አቆሙ ማለት አይደለምና።

ቤተ መቅደስ እንዲሰሩላቸው የተጠየቁት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ምንም እንኳ ጥያቄው የተገባና ደገኛ ጥያቄ ቢሆንም ማንንም ሳያማክሩ በራሳቸው ውሳኔ መሠረት ጣሉ ግድግዳ ለስኑ ጣራ ክደኑ መስቀል አኑሩ ቤተ ክርስቲያን ተከሉ ብለው ወዲያው አላዘዙም። ከዛይ ይልቅ ወደ ወንድሞቻቸው ወደ ጴጥሮስና ወደ ዮሐንስ የፊልጵስዮስ አማኞች ቤተ መቅደስ እንድንሰራላቸው ጠየቁን ምን ይሻላል ? ብለው መልክት ላኩባቸው እነርሱም ያለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቃድ አንዳች ልታደርጎ አይገባም እናንተም ጸልዮ እኛም እንጸልያለን ብለው መለሱላቸው። ቤተ መቅደስ ዝም ተብላ አትሰራም፣ አትተከልም" ሁሉ በአግባቡና በሥርዓት ይሁን" እንደተባለ በአግባቡና በሥርዓት ልትሰራ ያስፈልጋታል 1ኛ ቆሮ 14፥40

#ቤተ_መቅደስ ወይም ቤተ እግዚአብሔር ለመሥራት በመጀመሪያ ፈቃደ እግዚአብሔርን በጾም በጸሎት መጠየቅ ይገባል ። እንደ ቅድስ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ አርብ በቀራኒዮ አደባባይ ለሰው ልጆች ቤዛ ሲል በመስቀሉ ብዙ ደም አፍስሷል ይህንንም ደም ቅዱስ ዑራኤል መላእክ በጽዋው ቀድቶ በብርሃን መነሳንስ ፍጥረት ዓለሙን ለመቀደስ ወደ ምድር እረጭቶታል። ታድያ ቤተ ክርስቲያን ስትሰራ ይህ የደሙ ነጠብጣብ ባለበት ወይም በነጠበበት ቦታ ላይ መሆን አለበት እስካሁን የተሰሩ ቤተ ክርስቲያናት ሁሉ እግዚአብሔር ባወቀ ለቅዱሳኑ በመግለጥ የተሰሩ ናቸው ታዲያ ይህን መሰሉን ቦታ ለማወቅ ከእግዚአብሔር ጋር በጸም በጸሎት መነጋገር ፍቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "ያለ እኔ አንዳች ልታደርጉ አይቻላችሁም" #ዮሐ 15÷5

ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስም የቅዱስ ጴጥሮስን እና የቅዱስ ዮሐንስ ምክር ተቀብለው በያሉበት ሱባዔ ያዙ ጾም ጸሎት በማድረግ ፍቃደ እግዚአብሔር ጠየቁ ሰባዔያቸውን ሲጨርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሩቅም ከቅርብም ያሉ ሐዋርያቱን በደመና እየጫነ በፊልጵስዮስ ከተማ ሰበሰባቸው። ቅዱስ ዮሐንስም ጌታዬ ስለምን ሰበሰብከን ብሎ ጠየቀው በእናቴ ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰራ ፍቃዴ ነው አሁንም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ሰበሰብኳቹ አለው።

#ከዚያም ምሳሌዋ ወደሆነው ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ወሰዳቸው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ሕዝቅኤት በትንቢቱ “ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ብሎ እንደጻፈ....።” #ት.ሕዝ 44፥1 በዚያም ተራርቀው የነበሩ ሦስት ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቧ ቁመቱን ወርዱን መጥኞ ሰጣቸው እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው ሳለ እየለመለመ ቁመቱ 24 ወርዱም12 ክንድ አድርጎ ሰርቶ አሳይቷቸዋል።

"ወይዜኒ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ" እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ ብሏቸው ዐረገ ። ዛሬም በቅድስሀ ቅዱሳን በእናቱና በድንግል ማርያም ስም እና በቅዱሳኑ ሰም ለምን ቤተ መቅደስ ትሠራላችሁ ፣ ለምን ታቦት ትቀርጻላችሁ ለሚሉን ሁሉ ልጇ ሰርቶ ስላሳየንና ፍቃዱ ስለሆነ ይልቁኑ እናንተም እንዲሁ ሥሩ እንላቸዋለን ።“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።” #ኢሳ 56፥5

#ቤቴ አላት ቤተ ክርስቲያንን በቅጥሬም ውጥ አለ በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚታነጹ ጠቀል እና ጠበል ቤት፣ቤተ ልሔም ፣ ደውል ቤት ፣ሕሙማን ማረፊያ፣ ክርስትና ቤት ፍትሐት ቤት ግምጃ ቤት፣ወዘተ የመሳሰሉን በእናቴና በቅዱሳኖቼ ሰም ቢሰየም እወዳለው ፍቃዴ ነው ሲል ነው።


የእመቤታችን ቤተ ክርሰቲያን፣ የእመቤታችን ጽላት ፣የእመቤታችን ጠበል ፣የእመቤታችን እምነት ማለታችን ትክክል የሆነ ሁሉም በምስጢርና በምክንያት የሆነ ነው ።
#የጀመርነውን ለመጨረስ ያክል ሰኔ 20ቀን ጻሕጻ ቤተ ክርስቲያኗን ሰርቶ ከሰጣቸው በኋላ በማግስቱ ሰኔ 21ቀን በዛችሁ ቤተ መቅደስ እመቤታችንን መንበር ቅዱስ ጴጥሮስን ተራዲኢ ካህን(ንፍቅ) ካህን ፣ እስጢፋኖስን ሰራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል ።ዳግመኛም ቅዱስ ጴጥሮስን እጁን ጭኞ ፓትርያርክ አድርጎ ሾሞታል በዚህ ጊዜ ሰማያዊያን መላእክት ምድራዊያን ሐዋርያት በአንድነት ሆነው ይሰብሖ ለእግዚአብሔር እያሉ አመስግነዋል ።
______ይቆየን__________
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የልጇ የወዳጇ የኢየሱስ ክርስቶስም ቸርነት የቅዱሳኑም ሁሉ ረድኤትና በረከት አይለየን !

አ.አ ኢትዮጵያ
ሰኔ 21/2013 ዓ.ም
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#እኛ_አባቶቻችንን እንሰማለን እንታዘዛቸዋለንም !
|ድምጻቸውን እናውቀዋለንና
#ዮሐ 10÷3-5
አ.አ ልደታ ማርያም /ማኅደረ ስብሐት/ ቤ/ክ