#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ታክሲው ውስጥ የሚጮኸው ሙዚቃ ጭንቅላቱን በጠበጠው፡፡ማታ እንቅልፍ አልወስድህ ብሎት ሲጨነቅ ነበር ያደረው::
“ምንድነው የሆንከው? ለምን አትነግረኝም?” አለች ዘውዲቱ
ከሆቴል ገዝታ ካመጣችው ምግብ እያጎረሰችው፡፡ “ምስኪን አሁንስ ሚስትህ
ናፈቀችሁ መሰለኝ::
ያጎረሰችውን እያላመጠ ዝም አላት:: ወሬ አላሰኘውም:: ምግቡም እንዳያስከፋት ብሎ ነው እንጅ ቢቀርበት በወደደ፡፡
እራት በልተው ተጣጥበው መብራቱን አጥፍተው አልጋ ላይ ከወጡ በኋላ ናትናኤል በጀርባው እንደተንጋለለ አያኖቹን ጣሪያው ላይ ተክሎ ቀረ፡፡
ምን ሆና ይሆን? እንዴት ሁለት ቀን ሙሉ ስራ ሳትገባ ትቀራለች በጤናዋ ባትሆን ነው እንጅ:: ደግሞ ምህረት እቤቷ: ደወዬ
የሚያነሳ አጣሁ ማለቷ ምን ማለቷ ነው? ቤቷን ዘግታ የት ትሄዳለች? ምናልባት አሟት ወላጆቿጋ ሄዳ ይሆን እንዴ? የወላጆቿን ቤት ደግሞ አያውቀውም ! ጉለሌ እንደሆኑ ነግራዋለች፡፡ ግን በደፈናው ጉለሌ ተብሎ አይኬድ፡፡ ቤቷ ሄዶ ይሞክር ይሆን?
ሌሊቱን ሲጨነቅ አደረ፡፡ አሁን ደግሞ ታክሲው ውስጥ ያለው ሙዚቃ አይሉት ጩኽት
“ሲጋራ ፋብሪካ ነው ያሉኝ?” አለው ባለታክሲው፡፡
“እ? አዎ የኔ ልጅ፡፡ ከዚህ ይበቃኛል፡፡” ናትናኤል የታክሲውን በር ከፍቶ ወረደ፡፡
“አባ ገንዘበስ?!” ባለታክሲው የመኪናውን ጥሩንባ ተጭኖ ጮኹ፡፡
“ይቅርታ! ይቅርታ!” አለ ናትናኤል ከሄደበት ተመልሶ ከጋቢው ስር
ከደረት ኪሱ ገንብ እያወጣ “ይቅርታ የኔ ልጅ፡፡ ሃሳብ ገብቶኝ ተዘንግቶኝ
ነው::” ገንዘቡን ለባለታክሲው አቀበለው
ዘውዲቱ የገዛችላት ላስቲክ ቦት ጫማ መንገደኛ ቢያስመስለውም እላይ ከፈፉ እግሩን ከርክሮት ክፉኛ አቁስሎታል። በተራመደ ቁጥር የጫማው ክፈፍ ቁስሉን ሲነካበትና ሲፈትግበት ይለበልበዋል፡፡
ከመንገዱ ባሻገር የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ህንፃ ብቻውን ተገትሯል ... ሥራ ፈት፡፡ ናትናኤል ይህንን ፎቅ ሲመለከት ምንም ትርጉም አይሰጠውም በፎቁ ቅርፅ ውስጥ መልዕክት ካለ አንድ የሚል መሆን አለበት ቀጥ ያለ ፎቅ እንድ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን ከፎቁ ላይ ነቅሎ ሃሳቡን አሰባሰሰ፡፡ ለጥያቄው መፍትሄ የሚያገኝለት ካልቨርትን ቢያገኝ ብቻ እንደሆነ ከተረዳ ቆይቷል፡፡
ካልቨርትን : እግኝቶ የአውሬውን ማንነት ይፋ እስካላወጣ ድረስ የተደበቀውንና የተሸሸገውን ምሥጢር እስካላዝረከረከው ድረስ አንድ ቀን ከአንዱ ጥግ ነው የሚደፉት፡፡አብርሃምን እንደደፉት፡፡
ይህ ከመሆኑ በፊት ካልቨርትን ማግኘት አለበት፡፡ ግን ካልቨርትን ለማግኘት ከየት ሀ ብሎ እንደሚጀምር እንቆቅልሽ ሆነበት::
መረጃ የውስኪ ጠርሙስ ሾፌር ቤላ
መጠጥ ቤት…ሴት ሞሳድ ኤም አይ
ስድስት…ካዛንቺስ ወዳጁ ቤት… የሴት ልብስ ለብሶ ተሰወረ::
ቁልፉ የግድ እዚህ ውስጥ መሆን አለበት መፍትሄው እዚህ ውስጥ ከሌለ ካልቨርትን ሊያገኘው አይችልም:: ምክንያቱም እሱ የሚያውቀው ይህን ብቻ ነው አብርሃም የነገረውን፡፡
ያለጥርጥር ካልቨርት እንዲሰወር የካዛንቺሷ ወዳጁ ረድታዋለች፡፡ በመጨረሻ የታየው ከእሷ ቤት ሲወጣ ነው፡፡ ምናልባት የት እንደሚገኝም
ታውቅ ይሆናል፡፡ በተቻለው መንገድ ሴትየዋን ማግኘት አለበት:: ካልቨርትን
ለረዳው እንደሚፈልግ ሊያሳምናት ይገባል፡፡ ትጠረጥረው ይሆናል፡፡ ግን
ሊያሳምናት ከቻለና ካልቨርት ያለበትን ቦታ ከነገረችው ድብብቆሹ አበቃ ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜ ያለጥርጥር አውሬውን መረቡ ውስጥ ይከተዋል፡፡
ካልቨርት የሚያውቀው ነገር እንደሌለስ? ማወቅ አለበት ምንም የማያውቅ ከሆነ ለምን ተሸሽገ? ያውቃል፡፡ ለሕይወቱ የሚያሰጋው ምሥጢር ይዟል፡፡ ያንን ምስጢር ማግኘት አለበት፡፡ ካልቨርትን ለማግኘት ደግሞ መጀመሪያ የካዛንቺሷን ሴት አግኝቶ ማሳመን፤ ማግባባት ማሽነፍ፡፡፡ እሷ ብቻ ነች ዕድሉ፡፡
ግን አውሬው ለምን ሴትየዋን አቆያት? ያለጥርጥር ወደ ካልቨርት
የምትመሪ መንገድ ነች:: ይህንን ደግሞ አውሬው ሳያውቀው የሚቀር አያደለም:: ታዲያ ለምን አሰነበታት? ለምን አስገድዶም በሆን የካልቨርትን
እድራሻ አላወጣጣትም? ወያም ለማንኛውም ወገን ምሥጢሩን የካልቨርትን አድራሻ እንዳትጠቁም ለምን እንደ አብርሃም አሳስወገዳትም?
ምናልባት ሴትየዋ ራሷ ወጥመድ እንደሆነችስ? የካልቨርትን አድራሻ የሚያነፈንፍ፡ አይጥ ወደ ካዛንቺስ እንዲመጣና ከወጥመድ እንዲገባ
የተንጠለጠለች የሥጋ ቁራጭ እንደሆነችስ? ካዛንቺስ ከመድረሱ እንገቱን ቆርጠው ቢጥሉትስ?'፡ ናትናኤል ሰጋ:ዠ ኣብርሃም ያለው ትዝ አለው
“… ሁለቱን የክትትል ሰዎች ባሰማራን በሶስተኛው ቀን አንደኛው ሰዋችን በስለት ታርዶ እዛው ካዛንቺስ ቱቦ ውስጥ ተጥሎ ተገኘ.…”
ህ! “እዛው ካዛንቺስ” ወጥመድ
ያለጥርጥር ካዛንቺስ ወጥመድ ተጠምዶለታል፡፡ ቢሆንም ምርጫ
የለውም፡፡ ወደ ካልቨርት ሊቀርብ የሚችለው የካዛንቺሏን ሴት ሲያገኝ ብቻ
ነው:: የግድ ካዛንቺስ መሄድ አለበት፡፡
'ካዛንቺስ፡፡ ካዛንቺስ ምኑጋ? ካዛንቺስ ስንት አውራ መንገዶች አሉ?… ካዛንቺስ ስንት መጠጥ ቤቶች አሉ? የትኛዋ ነች የካልቨርት ወዳጅ? “የፈጣሪ ያለህ!' የካዛንቺስ ስፋቱና የቀሚስ ለባሹ ብዛት ታየው::
ሌላ ጥያቄ! እንዴት ሊያገኛት ይችላል? ማን ሊመራው ይችላል? አብርሃም ምንድነው ያለው.…?
የቅብብሎሹን ሠንሠለት መስበር ነው
ካልቨርት የሰረቀውን መረጃ…በውስኪ ጠርሙሶች…በሾፌርነት ለማያገለግል ኢትዮጵያዊ ያቀብላል..ሹፌሩ ቤላ መጠጥ ቤት ላላት.…”
ሹፌሩ ሹፌሩ ሌላ መጠጥ ቤት ያላትን ሴት ያውቃታል ማለት ነው፡፡ የካዛንቺሷንስ? ሊያውቃት ይችላል? ምናልባት ካልቨርት የሚቀርበው ከሆነ ሊያውቃት ያችላል፡፡ ያለው ምርጫ ሾፌሩ ነው:: ሾፌሩን አአግኝቶ የካዛንቺሷን ሴት እድራሻ እንዲሰጠው መጠየቅ::
ሾፌሩ የኛ ሰወ ነው በእሱ በኩል ነው
መረጃውን የምናገኘው...” ነበር ያለው
አብርሃም::
ሌላ ወጥመድ፡፡ ሾፌሩም አደገኛ ነው፡፡ ካዛንቺስ ያለችውን የካልቨርትን ወዳጅ ሆቴል ኣሳየኝ።” ሲለው መቼም መጠራጠሩ አይቀርም፡፡
“እሺ ና” ብሎ ገመድ አንገቱ ቢያስገባለትስ? መሬት ለመሬት እያንሻተተና እየጎተተ ቢያስይዘውስ? እርግጥ ያለው ምርጫ ወደ ካዛንቺሷ እመቤት የሚደርሰው ብቸኛ መንገድ የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ብቻ ነው:: ለይቶ የሚያውቀው አድራሻ የእርሱን ብቻ ነዋ! ቢሆንም ሰውየውን በአካል
መገናኘት የለበትም፡፡አንድ ዘዴ መፍጠር አለበት፡፡ ናትናኤል ለበርካታ ቀናቶች ሲያወጣ ሲያወርድ መልስ ሲሻለት የቆየው ጥያቄ ይህ ነበር፡፡መልሱን
አግኝቷል። አቅዶ ወጥኖ ጨርሷል፡፡ ትከሻው ላይ አላርፍልህ ያለውን ጋቢ
እያስተካከለ ከመንገድ ወዳለ ትንሽ ቁርስ ቤት ገባ፡፡
“የኔ ልጅ እባክሽ ስልክ ታስደውይኝ…እከፍላለሁ::ችግር አጋጥሞኝ ነው ልጅ ታማብኝ፡፡” አላቸው እናቱ የሚሆኑትን የቁርስ ቤቷን ባለቤት ጠጋ ብሎ። ያቀደውን ደረጃ በደረጃ ይፈጽም ጀመር፡፡
ሴትየዋ ስልክ ማስደወሉን ባይወዱትም ከቄስ ጋር! ከእግዚኣብሄር ሰው ጋር ክፉ መነጋገሩን አልፈለጉትም፡፡ ከባልኮኒው ስር አንድ ሰማያዊ ስልክ አውጥተው ቄሱ ፊት ቆለሉትና “ያው” ብለው ፊታቸውን አዙረው ሄዱ፡፡ · ደረታቸው ላይ የተቆለለው የጡት ተራራ የዘውዲቱን ጋራ
ያስንቃል፡፡
ናትናኤል ሴትየዋ ዞር እንዳሉለት የስልኩን መነጋገሪያ አንስቶ በመጀመሪያ ወደ ማዞሪያ ደውሎ የላይቤርያ ኤምባሲን የስልክ ቁጥር ከጠየቀና ካገኘ በኋላ ወደ ኤምባሲው ደወለ። በላይቤርያው ኤምባሲ ውስጥ ከአንድ በላይ ሾፌር ሊኖር ይችላል የትኛውን አቅርቡልኝ ሊል ነው? ብቻ ማናቸውም ቢሆኑ የካልቨርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ታክሲው ውስጥ የሚጮኸው ሙዚቃ ጭንቅላቱን በጠበጠው፡፡ማታ እንቅልፍ አልወስድህ ብሎት ሲጨነቅ ነበር ያደረው::
“ምንድነው የሆንከው? ለምን አትነግረኝም?” አለች ዘውዲቱ
ከሆቴል ገዝታ ካመጣችው ምግብ እያጎረሰችው፡፡ “ምስኪን አሁንስ ሚስትህ
ናፈቀችሁ መሰለኝ::
ያጎረሰችውን እያላመጠ ዝም አላት:: ወሬ አላሰኘውም:: ምግቡም እንዳያስከፋት ብሎ ነው እንጅ ቢቀርበት በወደደ፡፡
እራት በልተው ተጣጥበው መብራቱን አጥፍተው አልጋ ላይ ከወጡ በኋላ ናትናኤል በጀርባው እንደተንጋለለ አያኖቹን ጣሪያው ላይ ተክሎ ቀረ፡፡
ምን ሆና ይሆን? እንዴት ሁለት ቀን ሙሉ ስራ ሳትገባ ትቀራለች በጤናዋ ባትሆን ነው እንጅ:: ደግሞ ምህረት እቤቷ: ደወዬ
የሚያነሳ አጣሁ ማለቷ ምን ማለቷ ነው? ቤቷን ዘግታ የት ትሄዳለች? ምናልባት አሟት ወላጆቿጋ ሄዳ ይሆን እንዴ? የወላጆቿን ቤት ደግሞ አያውቀውም ! ጉለሌ እንደሆኑ ነግራዋለች፡፡ ግን በደፈናው ጉለሌ ተብሎ አይኬድ፡፡ ቤቷ ሄዶ ይሞክር ይሆን?
ሌሊቱን ሲጨነቅ አደረ፡፡ አሁን ደግሞ ታክሲው ውስጥ ያለው ሙዚቃ አይሉት ጩኽት
“ሲጋራ ፋብሪካ ነው ያሉኝ?” አለው ባለታክሲው፡፡
“እ? አዎ የኔ ልጅ፡፡ ከዚህ ይበቃኛል፡፡” ናትናኤል የታክሲውን በር ከፍቶ ወረደ፡፡
“አባ ገንዘበስ?!” ባለታክሲው የመኪናውን ጥሩንባ ተጭኖ ጮኹ፡፡
“ይቅርታ! ይቅርታ!” አለ ናትናኤል ከሄደበት ተመልሶ ከጋቢው ስር
ከደረት ኪሱ ገንብ እያወጣ “ይቅርታ የኔ ልጅ፡፡ ሃሳብ ገብቶኝ ተዘንግቶኝ
ነው::” ገንዘቡን ለባለታክሲው አቀበለው
ዘውዲቱ የገዛችላት ላስቲክ ቦት ጫማ መንገደኛ ቢያስመስለውም እላይ ከፈፉ እግሩን ከርክሮት ክፉኛ አቁስሎታል። በተራመደ ቁጥር የጫማው ክፈፍ ቁስሉን ሲነካበትና ሲፈትግበት ይለበልበዋል፡፡
ከመንገዱ ባሻገር የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ህንፃ ብቻውን ተገትሯል ... ሥራ ፈት፡፡ ናትናኤል ይህንን ፎቅ ሲመለከት ምንም ትርጉም አይሰጠውም በፎቁ ቅርፅ ውስጥ መልዕክት ካለ አንድ የሚል መሆን አለበት ቀጥ ያለ ፎቅ እንድ፡፡
ናትናኤል አይኖቹን ከፎቁ ላይ ነቅሎ ሃሳቡን አሰባሰሰ፡፡ ለጥያቄው መፍትሄ የሚያገኝለት ካልቨርትን ቢያገኝ ብቻ እንደሆነ ከተረዳ ቆይቷል፡፡
ካልቨርትን : እግኝቶ የአውሬውን ማንነት ይፋ እስካላወጣ ድረስ የተደበቀውንና የተሸሸገውን ምሥጢር እስካላዝረከረከው ድረስ አንድ ቀን ከአንዱ ጥግ ነው የሚደፉት፡፡አብርሃምን እንደደፉት፡፡
ይህ ከመሆኑ በፊት ካልቨርትን ማግኘት አለበት፡፡ ግን ካልቨርትን ለማግኘት ከየት ሀ ብሎ እንደሚጀምር እንቆቅልሽ ሆነበት::
መረጃ የውስኪ ጠርሙስ ሾፌር ቤላ
መጠጥ ቤት…ሴት ሞሳድ ኤም አይ
ስድስት…ካዛንቺስ ወዳጁ ቤት… የሴት ልብስ ለብሶ ተሰወረ::
ቁልፉ የግድ እዚህ ውስጥ መሆን አለበት መፍትሄው እዚህ ውስጥ ከሌለ ካልቨርትን ሊያገኘው አይችልም:: ምክንያቱም እሱ የሚያውቀው ይህን ብቻ ነው አብርሃም የነገረውን፡፡
ያለጥርጥር ካልቨርት እንዲሰወር የካዛንቺሷ ወዳጁ ረድታዋለች፡፡ በመጨረሻ የታየው ከእሷ ቤት ሲወጣ ነው፡፡ ምናልባት የት እንደሚገኝም
ታውቅ ይሆናል፡፡ በተቻለው መንገድ ሴትየዋን ማግኘት አለበት:: ካልቨርትን
ለረዳው እንደሚፈልግ ሊያሳምናት ይገባል፡፡ ትጠረጥረው ይሆናል፡፡ ግን
ሊያሳምናት ከቻለና ካልቨርት ያለበትን ቦታ ከነገረችው ድብብቆሹ አበቃ ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜ ያለጥርጥር አውሬውን መረቡ ውስጥ ይከተዋል፡፡
ካልቨርት የሚያውቀው ነገር እንደሌለስ? ማወቅ አለበት ምንም የማያውቅ ከሆነ ለምን ተሸሽገ? ያውቃል፡፡ ለሕይወቱ የሚያሰጋው ምሥጢር ይዟል፡፡ ያንን ምስጢር ማግኘት አለበት፡፡ ካልቨርትን ለማግኘት ደግሞ መጀመሪያ የካዛንቺሷን ሴት አግኝቶ ማሳመን፤ ማግባባት ማሽነፍ፡፡፡ እሷ ብቻ ነች ዕድሉ፡፡
ግን አውሬው ለምን ሴትየዋን አቆያት? ያለጥርጥር ወደ ካልቨርት
የምትመሪ መንገድ ነች:: ይህንን ደግሞ አውሬው ሳያውቀው የሚቀር አያደለም:: ታዲያ ለምን አሰነበታት? ለምን አስገድዶም በሆን የካልቨርትን
እድራሻ አላወጣጣትም? ወያም ለማንኛውም ወገን ምሥጢሩን የካልቨርትን አድራሻ እንዳትጠቁም ለምን እንደ አብርሃም አሳስወገዳትም?
ምናልባት ሴትየዋ ራሷ ወጥመድ እንደሆነችስ? የካልቨርትን አድራሻ የሚያነፈንፍ፡ አይጥ ወደ ካዛንቺስ እንዲመጣና ከወጥመድ እንዲገባ
የተንጠለጠለች የሥጋ ቁራጭ እንደሆነችስ? ካዛንቺስ ከመድረሱ እንገቱን ቆርጠው ቢጥሉትስ?'፡ ናትናኤል ሰጋ:ዠ ኣብርሃም ያለው ትዝ አለው
“… ሁለቱን የክትትል ሰዎች ባሰማራን በሶስተኛው ቀን አንደኛው ሰዋችን በስለት ታርዶ እዛው ካዛንቺስ ቱቦ ውስጥ ተጥሎ ተገኘ.…”
ህ! “እዛው ካዛንቺስ” ወጥመድ
ያለጥርጥር ካዛንቺስ ወጥመድ ተጠምዶለታል፡፡ ቢሆንም ምርጫ
የለውም፡፡ ወደ ካልቨርት ሊቀርብ የሚችለው የካዛንቺሏን ሴት ሲያገኝ ብቻ
ነው:: የግድ ካዛንቺስ መሄድ አለበት፡፡
'ካዛንቺስ፡፡ ካዛንቺስ ምኑጋ? ካዛንቺስ ስንት አውራ መንገዶች አሉ?… ካዛንቺስ ስንት መጠጥ ቤቶች አሉ? የትኛዋ ነች የካልቨርት ወዳጅ? “የፈጣሪ ያለህ!' የካዛንቺስ ስፋቱና የቀሚስ ለባሹ ብዛት ታየው::
ሌላ ጥያቄ! እንዴት ሊያገኛት ይችላል? ማን ሊመራው ይችላል? አብርሃም ምንድነው ያለው.…?
የቅብብሎሹን ሠንሠለት መስበር ነው
ካልቨርት የሰረቀውን መረጃ…በውስኪ ጠርሙሶች…በሾፌርነት ለማያገለግል ኢትዮጵያዊ ያቀብላል..ሹፌሩ ቤላ መጠጥ ቤት ላላት.…”
ሹፌሩ ሹፌሩ ሌላ መጠጥ ቤት ያላትን ሴት ያውቃታል ማለት ነው፡፡ የካዛንቺሷንስ? ሊያውቃት ይችላል? ምናልባት ካልቨርት የሚቀርበው ከሆነ ሊያውቃት ያችላል፡፡ ያለው ምርጫ ሾፌሩ ነው:: ሾፌሩን አአግኝቶ የካዛንቺሷን ሴት እድራሻ እንዲሰጠው መጠየቅ::
ሾፌሩ የኛ ሰወ ነው በእሱ በኩል ነው
መረጃውን የምናገኘው...” ነበር ያለው
አብርሃም::
ሌላ ወጥመድ፡፡ ሾፌሩም አደገኛ ነው፡፡ ካዛንቺስ ያለችውን የካልቨርትን ወዳጅ ሆቴል ኣሳየኝ።” ሲለው መቼም መጠራጠሩ አይቀርም፡፡
“እሺ ና” ብሎ ገመድ አንገቱ ቢያስገባለትስ? መሬት ለመሬት እያንሻተተና እየጎተተ ቢያስይዘውስ? እርግጥ ያለው ምርጫ ወደ ካዛንቺሷ እመቤት የሚደርሰው ብቸኛ መንገድ የላይቤርያው ኤምባሲ ሾፌር ብቻ ነው:: ለይቶ የሚያውቀው አድራሻ የእርሱን ብቻ ነዋ! ቢሆንም ሰውየውን በአካል
መገናኘት የለበትም፡፡አንድ ዘዴ መፍጠር አለበት፡፡ ናትናኤል ለበርካታ ቀናቶች ሲያወጣ ሲያወርድ መልስ ሲሻለት የቆየው ጥያቄ ይህ ነበር፡፡መልሱን
አግኝቷል። አቅዶ ወጥኖ ጨርሷል፡፡ ትከሻው ላይ አላርፍልህ ያለውን ጋቢ
እያስተካከለ ከመንገድ ወዳለ ትንሽ ቁርስ ቤት ገባ፡፡
“የኔ ልጅ እባክሽ ስልክ ታስደውይኝ…እከፍላለሁ::ችግር አጋጥሞኝ ነው ልጅ ታማብኝ፡፡” አላቸው እናቱ የሚሆኑትን የቁርስ ቤቷን ባለቤት ጠጋ ብሎ። ያቀደውን ደረጃ በደረጃ ይፈጽም ጀመር፡፡
ሴትየዋ ስልክ ማስደወሉን ባይወዱትም ከቄስ ጋር! ከእግዚኣብሄር ሰው ጋር ክፉ መነጋገሩን አልፈለጉትም፡፡ ከባልኮኒው ስር አንድ ሰማያዊ ስልክ አውጥተው ቄሱ ፊት ቆለሉትና “ያው” ብለው ፊታቸውን አዙረው ሄዱ፡፡ · ደረታቸው ላይ የተቆለለው የጡት ተራራ የዘውዲቱን ጋራ
ያስንቃል፡፡
ናትናኤል ሴትየዋ ዞር እንዳሉለት የስልኩን መነጋገሪያ አንስቶ በመጀመሪያ ወደ ማዞሪያ ደውሎ የላይቤርያ ኤምባሲን የስልክ ቁጥር ከጠየቀና ካገኘ በኋላ ወደ ኤምባሲው ደወለ። በላይቤርያው ኤምባሲ ውስጥ ከአንድ በላይ ሾፌር ሊኖር ይችላል የትኛውን አቅርቡልኝ ሊል ነው? ብቻ ማናቸውም ቢሆኑ የካልቨርት
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዴሪክ ዊሊያምስ ከሀይ ሆፕ ካፌው ወጥቶ ስምንት ብሎክ ወደሚቀርበው ሴንተሊና ውስጥ ወደሚገኘው ቢሮው ለመሄድ መኪናውን ሲያሽከረክር ከጠዋቱ አራት ሰዓት አልፎ ነበር። ቢሮው 12 ጫማ በ 8 ጫማ ስፋት ያለው ሆኖ መስኮት አልባ ነው፡፡ ነገር ግን ኪራዩ በጣም ርካሽ ስለሆነ እና የዋይፋይ ኢንተርኔቱ ጥሩ ስለሆነ ቢሮው ተስማምቶታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ከፎቁ ሥር የሚገኙት ወዳጆቹ የብረት ጎማ ስላላቸው ደምበኞቹ አስቸጋሪ በሚሆኑበት ጊዜ አስፈላጊውን እገዛ ያደርጉለታል፡፡
የአሁኗ ደንበኛው ያን ያክል አስቸጋሪ አይደለችም፡፡ ለሦስት ሰዓታት ያህል ቁጭ ብላ ስታወራው ዴሪክ ሦስት ነገሮች ለመገንዘብ ችሏል፡፡
የመጀመሪያው ነጥብ በትክክል እጁ ላይ ያለውን ካርዶችን በአግባቡ የሚጫወትበት ከሆነ በሥራው በጣም ብዙ ገንዘብ ያገኝበታል፡፡
ሁለተኛው ነገር ደግሞ ዕድሉ ከሆነ እና ከተሳካለት የድሮ ጠላቶቹ የሆኑትን የሎስ አንጀለስ ፖሊስ ዲፓርትመንት መበቀል ያስችለዋል::
ሦስተኛው ነገር ደግሞ ይሄ ጉዳይ ራሱን አደጋ ውስጥ ሊከተው የሚችል ነገር መሆኑ ነው።
ከሦስቱ ጉዳዩች በዋነኝነት የሳበው ነገር ቢኖር የሦስተኛው ጉዳይ ነው:: በጣም ከረዥም ጊዜ በኋላ ራሱ ላይ አደጋን የሚፈጥር ጉዳይ ሊገጥመው ነው። ትዳር ከመመስረቱ በፊት እንደዚህ ያሉ አደገኛ ጉዳዮች ላይ ነበር ይሰራ የነበረው። እናም ዛሬ ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ
ጉዳይዋን እንዲመረምርላት ስታናግረው የድሮው ማንነቱን ምን ያህል እንደናፈቀው
ነበር የተረዳው።
ማታ ላይ የጠጣው መጠጥ እና ጠዋት ላይ የበላው ቁርስ ሆዱ ውስጥ ቁጭ ስላለበት፣ እንዲፈጭለት ሁለት የአልካ ሲልትዘርን በትልቅ ብርጭቆ ውስጥ በሚገኝ የቧምቧ ውሃ ላይ ጨምሮ ጭልጥ አድርጎ ጠጣው። ከዴስኩ
ውስጥም የድሮ የማስታዋሻ ደብተር አውጥቶ መፃፍ ጀመረ፡፡ እንደ
ሁልጊዜም ሁሉ ሠረዝ ሠረዝ እያደረገ ከማንኛውም ደምበኛው የመጀመሪያ
ስብሰባ ካደረገ በኋላ በዚህ መልኩ ይፅፋል።
ወዲያውንም ገፆችን እየሞላ ማስታወሻውን መያዝ ጀመረ።
ኒኪ ሮበርትስ የምታስገርም ሴት ናት። በተለይ ደግሞ ለፖሊሶች ያልነገራቻቸውን ሚስጥሮቿን ለእሱ መንገሯ ጉዳይዋን ከፖሊሶቹ ቀድሞ ሊቋጭላት ያስችለዋል። እሷ እንዲፈታላት የፈለገችውን ነገር ለሁለት ከፍሎ ምርመራ መጀመሩ
ገቢውን ስለሚጨምርለት የተደራደራት። እሷም በእሱ ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ተስማምታ ሌሎች ሰዎችን
በዚህ መልኩ ነበር ከሚያስከፍለው በእጥፍ ሂሳብ ሲጠይቃት ጭምር ያለማንገራገር ለዚያውም ከነ ቦነሱ ነበር ቼክ የፃፈችለት።
“ባልሽ ከትዳር ውጪ ስላለው የፍቅር ግንኙነት ለማወቅ ትፈልጊያለሽ አይደል? ማለትም ሴትየዋ ማን እንደሆነች፣ እንዴት እንደተገናኙ እና ከእሷ ጋር የተያያዙትን ነገሮች ሁሉ ማወቅ እፈልጋለሁ ብለሻል?” ብሎ ጠየቃት።
“ልክ ነው” ብላ መለሰችለት ኒኪ
“መልካም እሱ የመጀመሪያው ጉዳይሽ ነው። ሌላኛው ደግሞ ግድያዎቹን
በተመለከተ እና አንቺ ላይ የግድያ ማስፈራሪያ እየተደረገብሽ ስላለ ጉዳይ
ነው። ከእነዚህ ግድያዎች በስተጀርባ ያለውን ሰው ልታውቂ ትፈልጊያለሽ።
ይሄ ደግሞ እኔ የኤል.ኤ.ፒ.ዲ ሥራን እንድሠራላቸው ትፈልጊያለሽ ማለት
ነው?”
“በትክክል”
“ይሄ ደግሞ ሁለተኛው ጉዳይሽ ነው” ብሎ ለእያንዳንዱ ጉዳዮቿ ዋጋ አውጥቶ ሲጠይቃት ኒኪ የወር ወጪውን በእጥፍ ዋጋ ነበር ቼኳ ላይ ፅፋ የሰጠችው። በዚህም የተነሳ ይህቺን ሴት በእውነቱ ሳይወዳት አይቀርም፡፡
ቢሮው ገብቶ ስለ ሁለቱ ጉዳዮች ሲያስብ የመጀመሪያው ባሏ ውሽማ ጉዳይ ገንዘብን የሚያልብበት ጉዳዩ እንደ ሆነ ገባው:: ምክንያቱም የኤል.ኤፒዲ ፖሊሶች ስለ ዶውግ ውሽማ ማንነት የሚያጣሩበት አንድም ምክንያት የላቸውም እና እሱ ጉዳዩን እስከፈለገው ጊዜ ድረስ በመጎተት የማያቋርጥ የገቢ ምንጩ ማድረግ ይችላል። በምዕራባዊ ሎስ አንጀለስ ውስጥ በዝሙት ዙሪያ ያሉ ጉዳዮች በሙሉ በጣም ምርጥ የገቢ ምንጭ የሚያስገኙለት ጉዳዮቹ ናቸው እና አምላኩን ያመሰግናል።
በግድያዎቹ ዙሪያ ላይ የሚያደርገው የግል ምርመራ ግን ያን ያህል የብዙ ጊዜው አስተማማኝ የገቢ ምንጩ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም
ምናልባት ይህንን ወር እንኳን ሳይጨርስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ የሊዛ ፍላንገን እና
የትሬቨን ሬይሞንድን ገዳዮችን ይዘው ለፍርድ ማቅረብ ይችላሉ። ምናልባት
ፖሊሶቹ በፍጥነት ጉዳዩን እንዳይቋጩ የሚያደርጋቸው ነገሮች ቢኖሩ
ዶክተሯን በመኪና ገጭቶ ሊያመልጥ የሞከረውን ገዳይ መከታተል ችላ
ማለታቸው አንደኛው ነው፡፡ ሁለተኛው ነገር ደግሞ ኒኪ በፖሊሶቹ ላይ
ሙሉ እምነት ስለሌላቸው የግድያ ማስፈራሪያ የኢ-ሜይል መልዕክቷን
እንኳን አምጥታ ለእሱ (ላዊሊያምስ) ማስረከቧ ነው።
ይሄ ደግሞ ሌላ ምርጥ ምልክት ነው፡፡ በጣም ብዙ መረጃዎችን በጉዳዩ
ዙሪያ መሰብሰብ እስከቻለ ድረስ ከኤል.ኤ.ፒ.ዲ ቀድሞ ምርመራውን በድል ማጠናቀቅ የሚችልበትን ዕድል ይፈጥርለታል፡፡
ከባሏ ውሽማ ይልቅ የሊዛ እና የትሬይ ግድያዎች ጉዳይ እሱን በደንብ የሳበው ሌላኛው ነገር ነው:: እንደ ሁሉም የሎስ አንጀለስ ነዋሪ ሁሉ ዴሪክም ቢሆን የግድያዎቹን ዜናዎች በደንብ ይከታተል ነበር፡፡ የኒኪ ሮበርትስ ታካሚ የሆነችው ቆንጆዋ ሞዴል ሊዛ ፍላንገን በአሰቃቂ ሁኔታ ሰውነቷ ተቆራርጦ እና ልቧ ላይ በጩቤ ተወግታ ህይወቷ አልፏል። ሊዛ
ትሬይ ሊዛ አፍሪካ አሜሪካዊው
ከተገደለች ከሦስት ቀናት በኋላም
በተገደለችበት በተመሳሳይ ሁኔታ ለመገደል በቅቷል። በመጀመሪያ ላይ በሊዛ ጥፍር ውስጥ የተገኘው የሞተ ሰው ህዋስን በማስመልከት ዞምቢው ነፍሰ ገዳይ በሚል ርዕስ በየማህበራዊ ገፆች ላይ ሲሰራጭ የነበረው ዜና
በመጨረሻ ላይም በዋነኛ የሚዲያ ተቋማት ላይ በዜና መልክ ቀርቦም
ተመልክቶታል፡፡ ሰዎች በእውነተኛው ዓለም ላይ እንደዚህ አይነት ነገር አለ
ብለው ማመናቸውን በወቅቱ ዴሪክን አስቆት ነበር፡፡ ያም ቢሆን ግን እስከ
አሁን ድረስ ጉዳዩን አወሳስቦታል።
“እና እስከ አሁን ድረስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ በግድያው ጠርጥሮ የያዘው አንድም
ሰው የለማ?” ብሎ ዴሪክ ኒኪን ጠየቋት ነበር፡፡
“እስከ አሁን ድረስ የለም። እንዲያውም አንደኛው ጆንሰን የተባለው መርማሪ ፖሊስ እኔን እንደ ገዳይ ሁሉ ይጠረጥረኛል፡፡ ባገኘኝ እና ባወራኝ
ቁጥርም እኔን የሚያወራኝ ልክ እንደ ወንጀለኛ ነው::”
“ይሄንን ባያደርግ አይገርመኝም፡፡ ሁሉም ፖሊሶች ባለጌዎች ናቸው፡፡” ብሎ ዴሪክ መለሰላት፡፡
“ሁሉም እንኳን አይደሉም ብላ ኒኪ አሰበች፡፡ ይህን ሀሳቧን ግን ለዊሊያምስ አልነገረችውም። በመቀጠልም ዊሊያምስን ያስገረመ አንድ ነገር
እንደደበቀቻቸው ነገረችው።
“ብራንዶን ግሮልሽ የሚባል ልጅ አውቅ እንደሆነ ጠይቀውኝ ነበር። ነገር
ግን አላውቅም ብዬ ነው የመለስኩላቸው፡፡ ልጁን አውቀው ነበር። ባለቤቱ እኔ ህክምና እንዳደርግለት ወደ እኔ ቢሮ ይዞት መጥቶ ነበር::”
“ለምንድነው ስለ እዚህ ልጅ የጠየቁሽ? አንቺስ ለምን ዋሸሻቸው?” ብሎ
ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
ኒኪም ትከሻዋን ሰበቀች እና “ለምን እንደጠየቁኝ አላውቅም። ምናልባት
ግን ልጁ ከግድያዎች ጋር የተያያዘ ነገር አለው ብለው እንደሚያስቡ ገምቻለሁ። ይሄውልህ ይሄ ብራንዶን የተባለ ልጅ እንደዚህ አይነት ነገርን የማድረግ አቅም የለውም፡፡ ልጁ በጣም ጨዋ እና መልካም ልጅ ነበር::" ብላ ፈገግ በማለት
አሁን ላይ ሳስበው ግን ልጁን አላውቀውም ብዬ የዋሸሁለት ከእነርሱ
ልከላከለው አስቤ ይመስለኛል”
“ፖሊሶቹ መዋሸትሽን ቢደርሱበት መረጃን በመደበቅ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዴሪክ ዊሊያምስ ከሀይ ሆፕ ካፌው ወጥቶ ስምንት ብሎክ ወደሚቀርበው ሴንተሊና ውስጥ ወደሚገኘው ቢሮው ለመሄድ መኪናውን ሲያሽከረክር ከጠዋቱ አራት ሰዓት አልፎ ነበር። ቢሮው 12 ጫማ በ 8 ጫማ ስፋት ያለው ሆኖ መስኮት አልባ ነው፡፡ ነገር ግን ኪራዩ በጣም ርካሽ ስለሆነ እና የዋይፋይ ኢንተርኔቱ ጥሩ ስለሆነ ቢሮው ተስማምቶታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ከፎቁ ሥር የሚገኙት ወዳጆቹ የብረት ጎማ ስላላቸው ደምበኞቹ አስቸጋሪ በሚሆኑበት ጊዜ አስፈላጊውን እገዛ ያደርጉለታል፡፡
የአሁኗ ደንበኛው ያን ያክል አስቸጋሪ አይደለችም፡፡ ለሦስት ሰዓታት ያህል ቁጭ ብላ ስታወራው ዴሪክ ሦስት ነገሮች ለመገንዘብ ችሏል፡፡
የመጀመሪያው ነጥብ በትክክል እጁ ላይ ያለውን ካርዶችን በአግባቡ የሚጫወትበት ከሆነ በሥራው በጣም ብዙ ገንዘብ ያገኝበታል፡፡
ሁለተኛው ነገር ደግሞ ዕድሉ ከሆነ እና ከተሳካለት የድሮ ጠላቶቹ የሆኑትን የሎስ አንጀለስ ፖሊስ ዲፓርትመንት መበቀል ያስችለዋል::
ሦስተኛው ነገር ደግሞ ይሄ ጉዳይ ራሱን አደጋ ውስጥ ሊከተው የሚችል ነገር መሆኑ ነው።
ከሦስቱ ጉዳዩች በዋነኝነት የሳበው ነገር ቢኖር የሦስተኛው ጉዳይ ነው:: በጣም ከረዥም ጊዜ በኋላ ራሱ ላይ አደጋን የሚፈጥር ጉዳይ ሊገጥመው ነው። ትዳር ከመመስረቱ በፊት እንደዚህ ያሉ አደገኛ ጉዳዮች ላይ ነበር ይሰራ የነበረው። እናም ዛሬ ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ
ጉዳይዋን እንዲመረምርላት ስታናግረው የድሮው ማንነቱን ምን ያህል እንደናፈቀው
ነበር የተረዳው።
ማታ ላይ የጠጣው መጠጥ እና ጠዋት ላይ የበላው ቁርስ ሆዱ ውስጥ ቁጭ ስላለበት፣ እንዲፈጭለት ሁለት የአልካ ሲልትዘርን በትልቅ ብርጭቆ ውስጥ በሚገኝ የቧምቧ ውሃ ላይ ጨምሮ ጭልጥ አድርጎ ጠጣው። ከዴስኩ
ውስጥም የድሮ የማስታዋሻ ደብተር አውጥቶ መፃፍ ጀመረ፡፡ እንደ
ሁልጊዜም ሁሉ ሠረዝ ሠረዝ እያደረገ ከማንኛውም ደምበኛው የመጀመሪያ
ስብሰባ ካደረገ በኋላ በዚህ መልኩ ይፅፋል።
ወዲያውንም ገፆችን እየሞላ ማስታወሻውን መያዝ ጀመረ።
ኒኪ ሮበርትስ የምታስገርም ሴት ናት። በተለይ ደግሞ ለፖሊሶች ያልነገራቻቸውን ሚስጥሮቿን ለእሱ መንገሯ ጉዳይዋን ከፖሊሶቹ ቀድሞ ሊቋጭላት ያስችለዋል። እሷ እንዲፈታላት የፈለገችውን ነገር ለሁለት ከፍሎ ምርመራ መጀመሩ
ገቢውን ስለሚጨምርለት የተደራደራት። እሷም በእሱ ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ተስማምታ ሌሎች ሰዎችን
በዚህ መልኩ ነበር ከሚያስከፍለው በእጥፍ ሂሳብ ሲጠይቃት ጭምር ያለማንገራገር ለዚያውም ከነ ቦነሱ ነበር ቼክ የፃፈችለት።
“ባልሽ ከትዳር ውጪ ስላለው የፍቅር ግንኙነት ለማወቅ ትፈልጊያለሽ አይደል? ማለትም ሴትየዋ ማን እንደሆነች፣ እንዴት እንደተገናኙ እና ከእሷ ጋር የተያያዙትን ነገሮች ሁሉ ማወቅ እፈልጋለሁ ብለሻል?” ብሎ ጠየቃት።
“ልክ ነው” ብላ መለሰችለት ኒኪ
“መልካም እሱ የመጀመሪያው ጉዳይሽ ነው። ሌላኛው ደግሞ ግድያዎቹን
በተመለከተ እና አንቺ ላይ የግድያ ማስፈራሪያ እየተደረገብሽ ስላለ ጉዳይ
ነው። ከእነዚህ ግድያዎች በስተጀርባ ያለውን ሰው ልታውቂ ትፈልጊያለሽ።
ይሄ ደግሞ እኔ የኤል.ኤ.ፒ.ዲ ሥራን እንድሠራላቸው ትፈልጊያለሽ ማለት
ነው?”
“በትክክል”
“ይሄ ደግሞ ሁለተኛው ጉዳይሽ ነው” ብሎ ለእያንዳንዱ ጉዳዮቿ ዋጋ አውጥቶ ሲጠይቃት ኒኪ የወር ወጪውን በእጥፍ ዋጋ ነበር ቼኳ ላይ ፅፋ የሰጠችው። በዚህም የተነሳ ይህቺን ሴት በእውነቱ ሳይወዳት አይቀርም፡፡
ቢሮው ገብቶ ስለ ሁለቱ ጉዳዮች ሲያስብ የመጀመሪያው ባሏ ውሽማ ጉዳይ ገንዘብን የሚያልብበት ጉዳዩ እንደ ሆነ ገባው:: ምክንያቱም የኤል.ኤፒዲ ፖሊሶች ስለ ዶውግ ውሽማ ማንነት የሚያጣሩበት አንድም ምክንያት የላቸውም እና እሱ ጉዳዩን እስከፈለገው ጊዜ ድረስ በመጎተት የማያቋርጥ የገቢ ምንጩ ማድረግ ይችላል። በምዕራባዊ ሎስ አንጀለስ ውስጥ በዝሙት ዙሪያ ያሉ ጉዳዮች በሙሉ በጣም ምርጥ የገቢ ምንጭ የሚያስገኙለት ጉዳዮቹ ናቸው እና አምላኩን ያመሰግናል።
በግድያዎቹ ዙሪያ ላይ የሚያደርገው የግል ምርመራ ግን ያን ያህል የብዙ ጊዜው አስተማማኝ የገቢ ምንጩ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም
ምናልባት ይህንን ወር እንኳን ሳይጨርስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ የሊዛ ፍላንገን እና
የትሬቨን ሬይሞንድን ገዳዮችን ይዘው ለፍርድ ማቅረብ ይችላሉ። ምናልባት
ፖሊሶቹ በፍጥነት ጉዳዩን እንዳይቋጩ የሚያደርጋቸው ነገሮች ቢኖሩ
ዶክተሯን በመኪና ገጭቶ ሊያመልጥ የሞከረውን ገዳይ መከታተል ችላ
ማለታቸው አንደኛው ነው፡፡ ሁለተኛው ነገር ደግሞ ኒኪ በፖሊሶቹ ላይ
ሙሉ እምነት ስለሌላቸው የግድያ ማስፈራሪያ የኢ-ሜይል መልዕክቷን
እንኳን አምጥታ ለእሱ (ላዊሊያምስ) ማስረከቧ ነው።
ይሄ ደግሞ ሌላ ምርጥ ምልክት ነው፡፡ በጣም ብዙ መረጃዎችን በጉዳዩ
ዙሪያ መሰብሰብ እስከቻለ ድረስ ከኤል.ኤ.ፒ.ዲ ቀድሞ ምርመራውን በድል ማጠናቀቅ የሚችልበትን ዕድል ይፈጥርለታል፡፡
ከባሏ ውሽማ ይልቅ የሊዛ እና የትሬይ ግድያዎች ጉዳይ እሱን በደንብ የሳበው ሌላኛው ነገር ነው:: እንደ ሁሉም የሎስ አንጀለስ ነዋሪ ሁሉ ዴሪክም ቢሆን የግድያዎቹን ዜናዎች በደንብ ይከታተል ነበር፡፡ የኒኪ ሮበርትስ ታካሚ የሆነችው ቆንጆዋ ሞዴል ሊዛ ፍላንገን በአሰቃቂ ሁኔታ ሰውነቷ ተቆራርጦ እና ልቧ ላይ በጩቤ ተወግታ ህይወቷ አልፏል። ሊዛ
ትሬይ ሊዛ አፍሪካ አሜሪካዊው
ከተገደለች ከሦስት ቀናት በኋላም
በተገደለችበት በተመሳሳይ ሁኔታ ለመገደል በቅቷል። በመጀመሪያ ላይ በሊዛ ጥፍር ውስጥ የተገኘው የሞተ ሰው ህዋስን በማስመልከት ዞምቢው ነፍሰ ገዳይ በሚል ርዕስ በየማህበራዊ ገፆች ላይ ሲሰራጭ የነበረው ዜና
በመጨረሻ ላይም በዋነኛ የሚዲያ ተቋማት ላይ በዜና መልክ ቀርቦም
ተመልክቶታል፡፡ ሰዎች በእውነተኛው ዓለም ላይ እንደዚህ አይነት ነገር አለ
ብለው ማመናቸውን በወቅቱ ዴሪክን አስቆት ነበር፡፡ ያም ቢሆን ግን እስከ
አሁን ድረስ ጉዳዩን አወሳስቦታል።
“እና እስከ አሁን ድረስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ በግድያው ጠርጥሮ የያዘው አንድም
ሰው የለማ?” ብሎ ዴሪክ ኒኪን ጠየቋት ነበር፡፡
“እስከ አሁን ድረስ የለም። እንዲያውም አንደኛው ጆንሰን የተባለው መርማሪ ፖሊስ እኔን እንደ ገዳይ ሁሉ ይጠረጥረኛል፡፡ ባገኘኝ እና ባወራኝ
ቁጥርም እኔን የሚያወራኝ ልክ እንደ ወንጀለኛ ነው::”
“ይሄንን ባያደርግ አይገርመኝም፡፡ ሁሉም ፖሊሶች ባለጌዎች ናቸው፡፡” ብሎ ዴሪክ መለሰላት፡፡
“ሁሉም እንኳን አይደሉም ብላ ኒኪ አሰበች፡፡ ይህን ሀሳቧን ግን ለዊሊያምስ አልነገረችውም። በመቀጠልም ዊሊያምስን ያስገረመ አንድ ነገር
እንደደበቀቻቸው ነገረችው።
“ብራንዶን ግሮልሽ የሚባል ልጅ አውቅ እንደሆነ ጠይቀውኝ ነበር። ነገር
ግን አላውቅም ብዬ ነው የመለስኩላቸው፡፡ ልጁን አውቀው ነበር። ባለቤቱ እኔ ህክምና እንዳደርግለት ወደ እኔ ቢሮ ይዞት መጥቶ ነበር::”
“ለምንድነው ስለ እዚህ ልጅ የጠየቁሽ? አንቺስ ለምን ዋሸሻቸው?” ብሎ
ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
ኒኪም ትከሻዋን ሰበቀች እና “ለምን እንደጠየቁኝ አላውቅም። ምናልባት
ግን ልጁ ከግድያዎች ጋር የተያያዘ ነገር አለው ብለው እንደሚያስቡ ገምቻለሁ። ይሄውልህ ይሄ ብራንዶን የተባለ ልጅ እንደዚህ አይነት ነገርን የማድረግ አቅም የለውም፡፡ ልጁ በጣም ጨዋ እና መልካም ልጅ ነበር::" ብላ ፈገግ በማለት
አሁን ላይ ሳስበው ግን ልጁን አላውቀውም ብዬ የዋሸሁለት ከእነርሱ
ልከላከለው አስቤ ይመስለኛል”
“ፖሊሶቹ መዋሸትሽን ቢደርሱበት መረጃን በመደበቅ
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
በሐሰት ተገንብቶ በተለበጠ አካባቢ ሁሉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ተገንጥሉ ልዩ ትክክለኛ አካባቢ ለመፍጠር ከፍ ያለ ችግር ያጋጥመዋል።ሁሉም በየበኩሉ የየራሱን የኑሮ ማሳ እያዳበረ በሚያርስበትና በሚያዘምርበት
ትክክለኛ ዓላማና ግብ ማምራት እንጂ፣ ይኸ እንዲህ ነው፣ ያኛው እንዲያ
አካባቢ፣ የራስን ዶማ እና መሣሪያ ይዞ በመቀላቀል ቀስ በቀስ ወደሚመኙት
ነው እያሉ መጃጃል ወደፊት መራመድ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ ነው:: ልክ
ያልሆነው ነገር ሁሉ ወለል ብሎ ቢታየኝም በግል ስክበው የሰነበትኩት
አስተሳሰብ ለጊዜውም ቢሆን በአካባቢዬ አሮጌ ልማድ ተዋጠ።
ባለሁበት ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ተርፎታል፣ ሞልቶታል፣ እየተባለ ነገር ግን ዝቅ ብሎ መታየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለምና የአካባቢን አስተያየትና ግምት ለመለወጥ ሲባል የሚደረግ ልዩ ልዩ ጥረት አንድም ፈጽሞ መውደቂያ ወይም ለጊዜው ቀጥ ብሎ መቆሚያ ሊሆን ይችላል፡፡ ግላዊ ስምና ክብርን ለመጠበቅና ለማስከበር ሲባል የሚደረግ የስግብግብነት ውጣ ውረድ ሁሉ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ የሥቃይ ሸክም ነው::
በግል ሀብት ጥሪት ፍላጎት የቆሰለና የበለዘ ሕሊናን ለማንጻትና ለማዳን የሚደረግ ጥረት መሪርና አድካሚ ነው:: ከቤተሰቦቼ የሚደርስብኝን ትችትና የወጪ ገቢ ሐሜት ለመከላከል ያህል የሕሊናዬን ዓላማ ቅንጣት ታህል ችላ ብዪ ሕይወት ኣልባ ተራ ስሜን ለማዳን ስል አንዲት የተለየች የሐሳብና የተግባር ዘመቻ ጀመርኩ። ሌሎችን ለመምሰልና ላይ ላዩን እኩል ሆኜ ለመታየት ስል አንዲት ባገልግሎት ላይ ከዋለች አራት ዓመት ያህል ያለፋት ቮልስዋገን መኪና ከስንት የደላላ ንትርክ በኋላ ገዛሁ፡፡ በክፍያው ላይ እኔና ጉልላት ተረባረብንበት፡፡ የጠንቃቃ ሰው ንብረት ስለ ነበረች በየጊዜው በመሰናከል አላስቸገረችኝም፡፡
ኑሮዬን መለስ ብዬ እያየሁ «የሕይወት ቀላል ፍቺ ይህች ትሆን? ወይስ ራስን የማታለያ ስሕተት» እያልኩ ማሰብ አዲሱ ልማዱ ሆነ፡፡ መስሎ መታየትና በጉራ ተኮፍሶ መወጣጠርን ከዚህም ከዚያም ቀሠምኩ፡፡ አንዳንድ ቀን ያን መበስበሱ እየታወቀ ቀለም እንደተቀባ ግንድ ላይ ላዩን ያሽበረቀ አስመሳይ ኑሮዬን መለስ ብዬ ሳየው ጎምዛዛ ኀዘን ይስማኝና በረጅሙ እተክዛለሁ። በሳምንት አንድና ሁለት ቀን እያመሽሁ መግባትና ሳይበዛም
መጠጥ መጎንጨትን ኣዘወተርኩ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከጧቱ ሁለት ሰዓት የወጣሁ ጥምብዝ ብዬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ገባሁ።
የወዲያነሽ ያጋጠማትን ያልታሰበ ችግር ችላ «አይ ጌትዩ! ስንቱን ለፈለፍከው ! መንጋት አበይለው ነጋ» አለችኝ ሰክሬ በገባሁ ማግሥት አብረን ቁርስ ስንበላ፡፡ ከዚያ በመጥፎ ልማዳዊ እምነት ተበክሎ ካደገው ልቦናዩ ምን አስነዋሪ ነገር ወጥቶ ይሆን በማለት በጣም ሠጋሁ፡፡ ከጎኔ ተነሥታ በስተጀርባዬ ቆመች፡፡ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ሁሉ ፊት ለፊቴ ባለው የቁም ሳጥን መስታዋት እመለከት ነበር። እሷም ይህችኑ ብልሃቴን ደርሳበት ኖሮ በመስተዋቲቱ ውስጥ ስታየኝ ዐይን ለዐይን ተጋጨን። የያዝኩትን
የእንቁላል ጥብስ ለመጉረስ አፈን ከፈት ላደርግ ሣቄ አመለጠኝና ተንከተከትኩ፡፡ እጄን ስባ ጎረሰችብኝ፡፡ 'ጌትዬ” አለችኝ ጉርሻዩን ቀምታ የልቧን ካደረሰች በኋላ፡፡ «ይኸው ዛሬ አምስተኛህ መሆኑ ነው መሰል ካንተ አላውቅምና ለምኑም ለምኑም ቢሆን ጥሩ አይደለም። ጌታነህ ሰክሮ እንዲህ አለ መባል ደግሞ አንዳች የሚያህል ነውር ነው። በዚያ ላይ ውርደቱ? ቅሌቱ... ጌትዬ አፈር ስበላልህ! ባንዲት እንጨት ስሔድ አትጠጣ፡ መቼም
ይኸን ጉድህን ጋሼ ጉልላት ኣልሰማም እንጂ ቢሰማማ....» ብላ አዘኔታና
ምክሯን አደባልቃ ከነገረችኝ በኋላ የተዳፈረችኝ ስለ መሰላት ሳይታወቃት
ትከሻዬን በግንባሯ ጠረግ ጠረግ እድርጋ ልትሸሽ ስትል እጅዋን ይዤ
አስቀረኋት፡፡
«ለመሆኑ ክፉ ነገር ተናገርኩ እንዴ? ሆድ ያባውን... የሚሉት ነገር ነበረበት?... አልኳት።
«የተናገርከው ሁሉ ምኑም አልገባኝ። እነዚያኑ ቤተሰቦችህን ስትሰድብና ስታጥላላ ነው ያደርከው:: እኔንም አይዞሽ በርቺ ድሉ ያንቺ ነው፤ ያባትሽ ስም አሸናፊ ነው እንቺም አሸናፊ ትሆኛለሽ እያልክ
ስታጫውተኝ አመሽህ» ብላ እጅዋን ነጥቃኝ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
የገዛ ስሕተቴን ለማስተባበል ሳይሆን ለማመኻንት ያህል ከጓዳ መለስ
እንዳለች «ትላንትም በል በል ብለው፣ አጠጥተውኝ ነው እንጂ ከእንግዲህ
ወዲህ መጠጥ በረበት ኣልዞርም» አልኳትና ወደ ሥራዬ ሄድኩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሌሊቱ አብዛኛውን ክፍል በሐሳብ ስገላበጥ አሳለፍኩት፡፡ እሑድ ጧት ከቁርስ በኋላ ሽር አልኩ። ሰበሰቡ ላይ ቆም ብዬ የወዲያነሽን ጠራኋት።
ከወደ ውስጥ ከተፍ አለች፡፡ የምትለውን ለመስማት ያህል 'አይቆርጡን አይፈልጡን ነይ እስኪ ወላጆቼ ቤት ይዤሽ ልሂድ? እኔ እያለሁ ምንም
እትሆኚ» አልኳት፡፡
ከልቤ ስለ መሰላት ክው ብላ ደነገጠች፡፡ «እንዲህ ንገረኝና ይለይልኝ
እንጂ! እጄን ይዘህ አስገድለኛ! እንኳንስ ካንተ ጋር አብሬ እዚያች ቤት
ገብቼላቸውና መንገድ ላይ ያዩን ይሆን እያልኩ አካላቴ ይበጠቃል። ምን
ቅብጥ ልጄ! ይልቅስ ሂድ ይቅናህ!» ብላ በእርሷ አስተሳሰብ የልቧን ተናግሬ
እንዳበቃች መንገድ ገባሁ፡፡ ጠምዛዛው መንገድ ከዐይኗ እስከ ሰወረኝ ድረስ
የአጥር ግቢውን በር ተደግፋ በዐይኖቿ ሸንችኝ፡፡ መኪናዬን ከቀበና ድልድይ
በላይ አቁሜ በእግር ቀጠልኩ። የወላጆቼን ቤት ከረገጥኩ ሦስት ወር ያህል አልፎኝ ስለ ነበር በዱሮው ዘበኛ በአቶ በየነ ምትክ ሌላ ሰው ተቀጥረዋል።
አጠር ብለው ከወደ ዐይናቸው ላም ያሉ ጸጉረ ገብስማ ሽማግሌ ናቸው::
አያውቁኝም። ለመግባት ፍቃድ ጠየቅሁ። ደረታቸውን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥተው
ማንን ነው የምትፈልገው? ጌቶችና አሜቴ እንደሁ ቤተስኪያን ሊስሙ እንደ
ኤዱ አልተመለሱም፡፡ ቆየት ብለህ ተመልሰሀ ናና ነግሬልህ ትገባለህ» ብለው ፊታቸውን አዙረው ችላ አሉኝ፡፡ ቸልታቸው ስላበሳጨኝ ልጃቸውስ የለችም
እንዴ? እሷም ካለች ያው ነው» ብዬ ጠየቅኋቸው፡፡ በጥፊ የመታኋቸው ያህል
ብው ብለው ተናደዱ፡፡ «እንዴ! እንዴ! መች አበድኩና! አንተ ስለ እኔ
እንጀራ ምንቸገረህ! የዋዛ ቤት መስሎሃል! እዚች ቦታም አያውሉኝ!» አሉና ነገሩኝ፡፡ ቀባጥሬም ሆነ ማንነቴን አስረድቼ መግባት ስላልፈለግሁ ደጅ ደጁን እያልኩ ለመቆየት ወሰንኩ፡፡ በዚያው አካባቢ መለስ ቀለስ ስል የውብነሽ ባዘቶ የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሳ ስትመጣ አየኋት።አመጣጧ በእኔው ኣቅጣጫ ስለ ነበር ቆሜ ጠበቅኋት። ከሩቅ የጀመረው ፈገግታዋ አጠገቤ ስትደርስ ተራውን ለውብ ጥርሶቿ ለቀቀ፡፡ ከጋቢው ሥር እጅዋን ብቅ አድርጋ ጨበጠችኝ፡፡ ስሜቷን ለመሸንገል ያህል ሳምኳት፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ሽማግሌው ኣጠገብ ደረስን፡፡ ቀና ብለው ከእግር እስከ ራሴ አዩኝ። ይኸ ደግሞ የማን ነው? በሚል አስተያየት እየገረመሙኝ አልፈናቸው ገባን፡፡
በምድረ ግቢው ያሉት አበቦችና አትክልቶች በጣም ያማሩ መሰለኝ፡፡
ከየውብነሽ ጋር እያወራሁ ዐይኖቼ ካትክልቶቸ ላይ አልተነቀሉም፡፡ እነዚያ
ምን ጊዜም ሌላ መሄጂያና መግቢያ የሌላቸው የሚመስሉት ነባር ሠራተኞች
ናፍቆትን በሚገልጽ ፈገግታ እጅ ነሡኝ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ዛሬ የጌቶች
ልጅ ከየት መጡ?” እንደሚሉ ታወቀኝ፡፡ አንደኛዋ ሠራተኛ እማማ ወለተሩፋኤልማ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ እኔ ግን ገና ከልጅነቴ ጀምሮ አልወዳቸውም ነበር፡፡ ኣብሮ ከመኖር ብዛት የተነሣ
እናትና አባቴ እንደ "ገረድ አያዩዋቸውም፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
በሐሰት ተገንብቶ በተለበጠ አካባቢ ሁሉ አንድ ግለሰብ ብቻውን ተገንጥሉ ልዩ ትክክለኛ አካባቢ ለመፍጠር ከፍ ያለ ችግር ያጋጥመዋል።ሁሉም በየበኩሉ የየራሱን የኑሮ ማሳ እያዳበረ በሚያርስበትና በሚያዘምርበት
ትክክለኛ ዓላማና ግብ ማምራት እንጂ፣ ይኸ እንዲህ ነው፣ ያኛው እንዲያ
አካባቢ፣ የራስን ዶማ እና መሣሪያ ይዞ በመቀላቀል ቀስ በቀስ ወደሚመኙት
ነው እያሉ መጃጃል ወደፊት መራመድ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ ነው:: ልክ
ያልሆነው ነገር ሁሉ ወለል ብሎ ቢታየኝም በግል ስክበው የሰነበትኩት
አስተሳሰብ ለጊዜውም ቢሆን በአካባቢዬ አሮጌ ልማድ ተዋጠ።
ባለሁበት ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ተርፎታል፣ ሞልቶታል፣ እየተባለ ነገር ግን ዝቅ ብሎ መታየትን የመሰለ አሳሳቢ ነገር የለምና የአካባቢን አስተያየትና ግምት ለመለወጥ ሲባል የሚደረግ ልዩ ልዩ ጥረት አንድም ፈጽሞ መውደቂያ ወይም ለጊዜው ቀጥ ብሎ መቆሚያ ሊሆን ይችላል፡፡ ግላዊ ስምና ክብርን ለመጠበቅና ለማስከበር ሲባል የሚደረግ የስግብግብነት ውጣ ውረድ ሁሉ በሰው ሕይወት ውስጥ ትልቅ የሥቃይ ሸክም ነው::
በግል ሀብት ጥሪት ፍላጎት የቆሰለና የበለዘ ሕሊናን ለማንጻትና ለማዳን የሚደረግ ጥረት መሪርና አድካሚ ነው:: ከቤተሰቦቼ የሚደርስብኝን ትችትና የወጪ ገቢ ሐሜት ለመከላከል ያህል የሕሊናዬን ዓላማ ቅንጣት ታህል ችላ ብዪ ሕይወት ኣልባ ተራ ስሜን ለማዳን ስል አንዲት የተለየች የሐሳብና የተግባር ዘመቻ ጀመርኩ። ሌሎችን ለመምሰልና ላይ ላዩን እኩል ሆኜ ለመታየት ስል አንዲት ባገልግሎት ላይ ከዋለች አራት ዓመት ያህል ያለፋት ቮልስዋገን መኪና ከስንት የደላላ ንትርክ በኋላ ገዛሁ፡፡ በክፍያው ላይ እኔና ጉልላት ተረባረብንበት፡፡ የጠንቃቃ ሰው ንብረት ስለ ነበረች በየጊዜው በመሰናከል አላስቸገረችኝም፡፡
ኑሮዬን መለስ ብዬ እያየሁ «የሕይወት ቀላል ፍቺ ይህች ትሆን? ወይስ ራስን የማታለያ ስሕተት» እያልኩ ማሰብ አዲሱ ልማዱ ሆነ፡፡ መስሎ መታየትና በጉራ ተኮፍሶ መወጣጠርን ከዚህም ከዚያም ቀሠምኩ፡፡ አንዳንድ ቀን ያን መበስበሱ እየታወቀ ቀለም እንደተቀባ ግንድ ላይ ላዩን ያሽበረቀ አስመሳይ ኑሮዬን መለስ ብዬ ሳየው ጎምዛዛ ኀዘን ይስማኝና በረጅሙ እተክዛለሁ። በሳምንት አንድና ሁለት ቀን እያመሽሁ መግባትና ሳይበዛም
መጠጥ መጎንጨትን ኣዘወተርኩ፡፡ አንድ ቀን እሑድ ከጧቱ ሁለት ሰዓት የወጣሁ ጥምብዝ ብዬ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ተኩል ገባሁ።
የወዲያነሽ ያጋጠማትን ያልታሰበ ችግር ችላ «አይ ጌትዩ! ስንቱን ለፈለፍከው ! መንጋት አበይለው ነጋ» አለችኝ ሰክሬ በገባሁ ማግሥት አብረን ቁርስ ስንበላ፡፡ ከዚያ በመጥፎ ልማዳዊ እምነት ተበክሎ ካደገው ልቦናዩ ምን አስነዋሪ ነገር ወጥቶ ይሆን በማለት በጣም ሠጋሁ፡፡ ከጎኔ ተነሥታ በስተጀርባዬ ቆመች፡፡ የምታደርገውን እንቅስቃሴ ሁሉ ፊት ለፊቴ ባለው የቁም ሳጥን መስታዋት እመለከት ነበር። እሷም ይህችኑ ብልሃቴን ደርሳበት ኖሮ በመስተዋቲቱ ውስጥ ስታየኝ ዐይን ለዐይን ተጋጨን። የያዝኩትን
የእንቁላል ጥብስ ለመጉረስ አፈን ከፈት ላደርግ ሣቄ አመለጠኝና ተንከተከትኩ፡፡ እጄን ስባ ጎረሰችብኝ፡፡ 'ጌትዬ” አለችኝ ጉርሻዩን ቀምታ የልቧን ካደረሰች በኋላ፡፡ «ይኸው ዛሬ አምስተኛህ መሆኑ ነው መሰል ካንተ አላውቅምና ለምኑም ለምኑም ቢሆን ጥሩ አይደለም። ጌታነህ ሰክሮ እንዲህ አለ መባል ደግሞ አንዳች የሚያህል ነውር ነው። በዚያ ላይ ውርደቱ? ቅሌቱ... ጌትዬ አፈር ስበላልህ! ባንዲት እንጨት ስሔድ አትጠጣ፡ መቼም
ይኸን ጉድህን ጋሼ ጉልላት ኣልሰማም እንጂ ቢሰማማ....» ብላ አዘኔታና
ምክሯን አደባልቃ ከነገረችኝ በኋላ የተዳፈረችኝ ስለ መሰላት ሳይታወቃት
ትከሻዬን በግንባሯ ጠረግ ጠረግ እድርጋ ልትሸሽ ስትል እጅዋን ይዤ
አስቀረኋት፡፡
«ለመሆኑ ክፉ ነገር ተናገርኩ እንዴ? ሆድ ያባውን... የሚሉት ነገር ነበረበት?... አልኳት።
«የተናገርከው ሁሉ ምኑም አልገባኝ። እነዚያኑ ቤተሰቦችህን ስትሰድብና ስታጥላላ ነው ያደርከው:: እኔንም አይዞሽ በርቺ ድሉ ያንቺ ነው፤ ያባትሽ ስም አሸናፊ ነው እንቺም አሸናፊ ትሆኛለሽ እያልክ
ስታጫውተኝ አመሽህ» ብላ እጅዋን ነጥቃኝ ወደ ጓዳ ገባች፡፡
የገዛ ስሕተቴን ለማስተባበል ሳይሆን ለማመኻንት ያህል ከጓዳ መለስ
እንዳለች «ትላንትም በል በል ብለው፣ አጠጥተውኝ ነው እንጂ ከእንግዲህ
ወዲህ መጠጥ በረበት ኣልዞርም» አልኳትና ወደ ሥራዬ ሄድኩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሌሊቱ አብዛኛውን ክፍል በሐሳብ ስገላበጥ አሳለፍኩት፡፡ እሑድ ጧት ከቁርስ በኋላ ሽር አልኩ። ሰበሰቡ ላይ ቆም ብዬ የወዲያነሽን ጠራኋት።
ከወደ ውስጥ ከተፍ አለች፡፡ የምትለውን ለመስማት ያህል 'አይቆርጡን አይፈልጡን ነይ እስኪ ወላጆቼ ቤት ይዤሽ ልሂድ? እኔ እያለሁ ምንም
እትሆኚ» አልኳት፡፡
ከልቤ ስለ መሰላት ክው ብላ ደነገጠች፡፡ «እንዲህ ንገረኝና ይለይልኝ
እንጂ! እጄን ይዘህ አስገድለኛ! እንኳንስ ካንተ ጋር አብሬ እዚያች ቤት
ገብቼላቸውና መንገድ ላይ ያዩን ይሆን እያልኩ አካላቴ ይበጠቃል። ምን
ቅብጥ ልጄ! ይልቅስ ሂድ ይቅናህ!» ብላ በእርሷ አስተሳሰብ የልቧን ተናግሬ
እንዳበቃች መንገድ ገባሁ፡፡ ጠምዛዛው መንገድ ከዐይኗ እስከ ሰወረኝ ድረስ
የአጥር ግቢውን በር ተደግፋ በዐይኖቿ ሸንችኝ፡፡ መኪናዬን ከቀበና ድልድይ
በላይ አቁሜ በእግር ቀጠልኩ። የወላጆቼን ቤት ከረገጥኩ ሦስት ወር ያህል አልፎኝ ስለ ነበር በዱሮው ዘበኛ በአቶ በየነ ምትክ ሌላ ሰው ተቀጥረዋል።
አጠር ብለው ከወደ ዐይናቸው ላም ያሉ ጸጉረ ገብስማ ሽማግሌ ናቸው::
አያውቁኝም። ለመግባት ፍቃድ ጠየቅሁ። ደረታቸውን ለረፋዷ ፀሐይ ሰጥተው
ማንን ነው የምትፈልገው? ጌቶችና አሜቴ እንደሁ ቤተስኪያን ሊስሙ እንደ
ኤዱ አልተመለሱም፡፡ ቆየት ብለህ ተመልሰሀ ናና ነግሬልህ ትገባለህ» ብለው ፊታቸውን አዙረው ችላ አሉኝ፡፡ ቸልታቸው ስላበሳጨኝ ልጃቸውስ የለችም
እንዴ? እሷም ካለች ያው ነው» ብዬ ጠየቅኋቸው፡፡ በጥፊ የመታኋቸው ያህል
ብው ብለው ተናደዱ፡፡ «እንዴ! እንዴ! መች አበድኩና! አንተ ስለ እኔ
እንጀራ ምንቸገረህ! የዋዛ ቤት መስሎሃል! እዚች ቦታም አያውሉኝ!» አሉና ነገሩኝ፡፡ ቀባጥሬም ሆነ ማንነቴን አስረድቼ መግባት ስላልፈለግሁ ደጅ ደጁን እያልኩ ለመቆየት ወሰንኩ፡፡ በዚያው አካባቢ መለስ ቀለስ ስል የውብነሽ ባዘቶ የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሳ ስትመጣ አየኋት።አመጣጧ በእኔው ኣቅጣጫ ስለ ነበር ቆሜ ጠበቅኋት። ከሩቅ የጀመረው ፈገግታዋ አጠገቤ ስትደርስ ተራውን ለውብ ጥርሶቿ ለቀቀ፡፡ ከጋቢው ሥር እጅዋን ብቅ አድርጋ ጨበጠችኝ፡፡ ስሜቷን ለመሸንገል ያህል ሳምኳት፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዘን ሽማግሌው ኣጠገብ ደረስን፡፡ ቀና ብለው ከእግር እስከ ራሴ አዩኝ። ይኸ ደግሞ የማን ነው? በሚል አስተያየት እየገረመሙኝ አልፈናቸው ገባን፡፡
በምድረ ግቢው ያሉት አበቦችና አትክልቶች በጣም ያማሩ መሰለኝ፡፡
ከየውብነሽ ጋር እያወራሁ ዐይኖቼ ካትክልቶቸ ላይ አልተነቀሉም፡፡ እነዚያ
ምን ጊዜም ሌላ መሄጂያና መግቢያ የሌላቸው የሚመስሉት ነባር ሠራተኞች
ናፍቆትን በሚገልጽ ፈገግታ እጅ ነሡኝ፡፡ ውስጥ ውስጡን ግን ዛሬ የጌቶች
ልጅ ከየት መጡ?” እንደሚሉ ታወቀኝ፡፡ አንደኛዋ ሠራተኛ እማማ ወለተሩፋኤልማ በወላጆቼ ቤት ውስጥ ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ እኔ ግን ገና ከልጅነቴ ጀምሮ አልወዳቸውም ነበር፡፡ ኣብሮ ከመኖር ብዛት የተነሣ
እናትና አባቴ እንደ "ገረድ አያዩዋቸውም፡፡
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....በአርሲ ጠቅላይ ግዛት በጭላሎ አውራጃ በሄጦሳ ወረዳ ውስጥ የሚገኘው ኛሮ እንኳን ለአንድ ሽፍታ ይቅርና ለእልፍ አእላፍ ሽፍቶች መሽሽጊያ ሊሆን የሚችል ሰፊ ባህር ነው፡፡ ከትንንሽ ቁጥቋጦ ጀምሮ ሶስት ሰው እጅ ለእጅ ተያይዞ ቢያቅፋቸው የማይሞሉ ከመቶ አመታት በላይ እድሜን ያስቆጠሩ ግዙፍ አገር በቀል ዛፎች የተጠቀጠቁበት ዱር ከመሆኑም በላይ በውስጡ ያሉት እጅግ በርካታ የዱር አራዊቶች ላኛሮ አስተማማኝ የሽፍታ መኖሪያነት በቂ ምስክር ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ዘላይ አራዊት፣
በደረት የሚሳቡ፣ በጉድጓድ የሚኖሩ፣ በየድንጋዩ ውስጥ የሚሹሎከሎኩ
በብዛት ይገኙበታል።አጋዘን፣ ድኩላ፣ የሜዳ ፍየል፣ ሚዳቋ፣ ነብር፣
ከርከሮ፣ ሰስ፣ ቀበሮ፣ ጅብ፣ እባብ፣ ዘንዶ... የሚርመሰመሱበት የቀለጠ
ዱር ...
የሳለን ተራራ እንደሰንሰለት ተያይዞ ሽቅብ ሲታይ ሰማዩን አቅፎና ደግፎ ያቆመው ሲመስል ኛሮ ደግሞ የታችኛው የቆላው አገረ ገዥነቱን ያለተቀናቃኝ ይዞ ተንሰራፍቷል። የተማመነበትን ሙጥኝ ያለበትን ሽሽቶ የተደበቀበትን አሳልፎ እንደማይሰጥ በኩራት ደረቱን ነፍቶ የሚመሰክር ዱር..
ኛሮ ዳገቱ ላይ ቡልቅ እያለ ከመሬት ውስጥ የሚወጣው የእሳተ ገሞራው
ሲስ በአካባቢው አጠራር “አርቱ” ይባላል። መሬቱ ማስ፣ ማስ ይደረግና ጉድጓድ ከተበጀ በኋላ የጉድጓዱ አፍ በጋቢ ወይንም በቁርበት ይሽፈናል። ከዚያ ምን ያስፈልጋል? ከውስጡ ቁጭ ማለት ነው።በዚያ ትኩስ እሳተ ገሞራ ጢስ እየተቀቀሉ እንደ ቅቤ ሲቀልጡ እንደ ዥረት የሚንቆረቆረው ላብ ቆሻሻውን ሙልጭ አድርጎ ይዞት ይወጣል። በዘመናዊ አጠራር “ሳውና ባዝ እንደሚባለው መሆኑ ነው። ኛሮ ለቤተሰብ አባሎቹ ለተለያዩ የዱር አራዊቶች ገነት ነው፡፡ እንደ ፍላጎታቸው ሁሉንም ችሎ
አቻችሎ ይዟቸዋል፡፡ የሚጋጥ ሳር ለሚጠይቀው ከጨሌው ጀምሮ የሰው
አንገት እስከሚውጠው ሰንበሌጥ ድረስ አብቅሎለታል። ሥጋ ለሚፈልገው በውስጡ ያቀፋቸው ሳር በል አራዊቶች በሽበሽ ስለሆኑ አድፍጦ ጉብ ማለት ብቻ ነው የሚያስፈልገው እንጂ በኛሮ በኩል የተጓደለ ነገር የለም፡፡ ኛሮ የገባን ፈልጎ ማግኘት ቀይ ባህር ውስጥ የወደቀ ቀለበት ለማግኘት እንደመፈለግ ሆኖ ዋሻነቱ ይጋነንለታል፡፡
ፀሀይዋ ደማቅ ጨረሯን በመለገሷ ሙቀቷን ለመቋደስ የሚፈልጉ አራዊ
ቶች ከየዋሻው፣ ከየጢሻውና ከየድንጋዩ ውስጥ እየወጡ ብቅ ብቅ ማለት
ጀምረዋል። ከእነዚህ መካከል ኛሮ በአይነቱም ሆነ በአፈጣጠሩ ለየት
ያለውን በሁለት እግሩ ቆሞ የሚራመደውን አውሬ ከነጀሌዎቹ በቤተሰብ አባልነት ከመዘገባቸው ውሎ አድሯል። ጎንቻ ዘረፋውን በስውር በሌሊት ያከናውንና ወደ ሐሮ ጫካ ተመልሶ ይሰምጣል። ከተራ ሌብነት በደረጃ ዕድገት ሽፍታ ተብሏል፡፡
“ጎንቻ! ጎንቻ ጎንቻ” በበርካታ ሰዎች
አንደበት በፍርሃት የሚጠራ ገናና ስም ሆኗል። በድንገት እየተከስተ መአተ ቁጣውን ካወረደው በኋላ በፍጥነት ስለሚሰወር ስሙ ሲጠራ በፍርሃት የሚርበደበዱና ብርክ የሚይዛቸው ሰዎች ቁጥር እየበራከተ ሄዷል። የጎንቻ ስም ሲጠራ ወንዱ ሱሪው ሊከዳው ይዳዳዋል፡፡ ሴቱ ደግሞ “የጎንቻ አምላክ” ብሎ በፍርሀት ያመልክበት ጀምሯል፡፡ በዚህ ሁኔታ የጎንቻ ዝና ከዳር እስከ ዳር አስተጋባ፡፡ ያንን አስከፊ ወንጀል እያፋፋመው ሲሄድ በቸልታ የተመለከተው ሁሉ ቀስ በቀስ በመቅሰፍት ጅራፉ
እየተሸነቆጠ ነው፡፡ የሌላው ህመም ያልተሰማው “እኔ እስካልተነካሁ ድረስ ምን አገባኝ?” በሚል መንፈስ ተሸብቦ የኖረው ሁሉ ከባድ ችግር ውስጥ እየወደቀ መጥቷል። ገና በእንጭጩ በቁጥጥር ስር ማዋል ሲቻል ጎንቻን የቂም መበቀያ ለማድረግ የሁለት፣የሶስት፣ የአስርና የሃያ ዓመት ቂም እየፈለጉ “እገሌ በሙግት ከመሬቴ ከእርስቴ ነቅሎኛልና ንቀልልኝ ቢቻል በራሱ ላይ ባይቻል በንብረቱ፣ በልጆቹ፣ ወይንም ደግሞ በሚስቱ ላይ አደጋ ጣልልኝ፣ እገሌ በህዝብ ፊት ሰድቦ አዋርዶኛልና አዋርድልኝ።
ይህን ያክል ዋጋ እከፍልሃለሁ” የሚሉ አማላጅ የሚልኩ ስዎች እየበዙ
መጡና በትዕቢት ልቡን አሳበጡት። ጎንቻም በድርድር ገንዘብ እየተቀበለ ፍላጎታቸውን ለማሳካት ባደረገው ጥረት የብዙዎችን አንጀት አራሰ፡፡
አሁን ጎንቻ የዋሻውን ኑሮ እጅግ እየተላመደው መጥቷል። ከሰው ይልቅ
የአራዊት ጠረን ተዋህዶታል፡፡ ከሞቀ ቤት፣ ከሞቀ አልጋ ይልቅ አስፈሪውን ጨለማ፣ዋሻና ጢሻውን የሚመርጥ ሆኗል። ለሰው ልጅ ህይወት ያለው ግምት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ሄዶ የወፍ ያክል እንኳ ዋጋ ሊሰጠው አልቻለም፡፡ ምንም ቢሆን ግን ከአውሬነት ባህሪው ውስጥ ሰው የመሆን ፍጥረቱ ሙሉ ለሙሉ አልጠፋም ነበረና ዘወትር ዓለሚቱን ያስ
ታውሳታል፡፡ ዘወትር ዓለሚቱን ይራባል፡፡ ይናፍቃታል፡፡ ኛሮ ዋሻ ከገባ በኋላ አንድ ሁለት ጊዜ ጨለማን ተገን አድርጎና ራሱን ለውጦ ጎብኝቷታል፡፡ ይሄ ግን ለሱ በቂ አልነበረም፡፡ ምኞቱና ፍላጎቱ ምንግዜም ከአጠገቡ እንዳትለየው አብራው ጫካ እንድትኖር ነው። እሱ የጫካው ንጉሥ
እሷ ደግሞ ንግስት ሆና ያለ አዛዥ ያለተቆጣጣሪ እያዘዙ እየተቆጣጠሩ
እየነጠቀ እየቀማ በድሎት አብሯት መኖር ይፈልጋል። እንደፈለገው እየበላ እየጠጣ ጥጋብ ሲያንጠራራው፣ እንደ ተዋጊ ኮርማ እያነጠነጠ የወሲብ ፍላጎቱ ሲቀሰቀስ የዓለሚቱ ገላ አእምሮውን እስከሚስት ድረስ በዐይኑ ላይ ይሄድበታል...
በኛሮ ጫካ ውስጥ በጎኑ ጋደም ብሎ፣ ጎፈሬውን ወደ ፊትና ወደ ኋላ
አመሳቅሎ፣ ጠመንጃውን እንደሚሰስቱለት ህፃን ልጅ በደረቱ ሸጉጦ የጠዋቷን ፀሀይ ሙቀት በመጋራት ስለሚያከናውናቸው ተግባራት እቅድ
ያወጣል፣ ያወርዳል። የመልኩ ጥቁረት አይነሳ! ከጥቁር አዝሙድ ጋር ይቀራረባል፡፡ ቁመቱ ረዥም ነው፡፡ ጎንቻ! ጎንቻ!! ጎንቻ! የፍርሀት ጌታ!!... የሰቀቀን አምላክ! በበርካታ ህዝብ አንደበት የሚነገረው ዝናው ሰው መሆኑን እንዲጠራጠር አድርጎታል። “ቀላል እና ከባድ ዘረፋን በመለየት ቀላሉን የዘረፋ ትርዒት የሚንቅ ከባዱን የሚወድ፣ ፈታኝ በሆነ ዘረፋና ግድያ የሚረካ በጥቃቅን
ዘረፋና ሌብነት ላይ እጁን የማያስገባ ዝናው የተፈራ ሽፍታ ሆኖ ለመኖር
ራሱን አሳምኗል፡፡ ከኛሮ አልፎ ግዛቱን ወደ ሌላ አስፋፍቶ፣ ጀሌዎቹን
በእጥፍ ድርብ አበራክቶ ዘረፋውን በማጧጧፍ ሀብታም መሆንን እየተመኘ ነው።
ይሄ ምኞቱ እንደሚሳካ ደግሞ ጥርጥር አልነበረውም፡፡ በተለይ ሰሞኑን
መልእክት የላከበት ባላባት ምን ያክል ለቁም ነገር ተፈላጊ ሰው እየሆነ
መምጣቱን አረጋግጦለታል። ወላጅ አባቱ በቶላ ሞት ምክንያት ተበሳጭተው ራሳቸውን በራሳቸው ያጠፉ መሆናቸውን ከጀሌዎቹ አንደበት በሰማበት ዕለት የቀለደው ቀልድ ጀሌዎቹን ጭምር ያስደነገጠ ነበር። ተበድሮ
ያልመለሰለትን ገንዘብ ሊቀበለው ነው አብሮት የሄደው ከተቀበለው በኋላ
ተመልሶ ይመጣልና አታስቡ በማለት ሊያረጋጋቸው መሞከሩ አለቃቸው
ምን ያክል ጨካኝ ሰው እንደሆነ አረጋግጦላቸዋል። ጎንቻ በደም ስሩ
ውስጥ የሚዘዋወረው የወንጀል ዕፅ የመረዘው መራራ ደም ነበረና የባላባቱን ነገር ሲያብሰለስል ከቆየ በኋላ በአፋጣኝ ሄዶ ማንነቱን ሊያስመስ ክር ፈለገ፡፡ ከዚያም ወደ ጀሌዎቹ ዘወር አለና በደፈረሱት ዐይኖቹ አካባቢውን በመቃኘት ጊርቦን አናገረው፡፡
“ስማ ጊርቦ! የሽማግሌው ጉዳይ?!” አለው፡፡ ጊርቦ አለቃው ጎንቻን በጣም የሚያከብር የሚፈራም ሰው ነው፡፡ በተዘረፈ ንብረት ተሸካሚነትና በወንጀል ተባባሪነት ብቻ ሳይሆን ጠቃሚ መረጃዎችን በመስብስብ በኩል ለጎንቻ ቀኝ እጁ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....በአርሲ ጠቅላይ ግዛት በጭላሎ አውራጃ በሄጦሳ ወረዳ ውስጥ የሚገኘው ኛሮ እንኳን ለአንድ ሽፍታ ይቅርና ለእልፍ አእላፍ ሽፍቶች መሽሽጊያ ሊሆን የሚችል ሰፊ ባህር ነው፡፡ ከትንንሽ ቁጥቋጦ ጀምሮ ሶስት ሰው እጅ ለእጅ ተያይዞ ቢያቅፋቸው የማይሞሉ ከመቶ አመታት በላይ እድሜን ያስቆጠሩ ግዙፍ አገር በቀል ዛፎች የተጠቀጠቁበት ዱር ከመሆኑም በላይ በውስጡ ያሉት እጅግ በርካታ የዱር አራዊቶች ላኛሮ አስተማማኝ የሽፍታ መኖሪያነት በቂ ምስክር ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ዘላይ አራዊት፣
በደረት የሚሳቡ፣ በጉድጓድ የሚኖሩ፣ በየድንጋዩ ውስጥ የሚሹሎከሎኩ
በብዛት ይገኙበታል።አጋዘን፣ ድኩላ፣ የሜዳ ፍየል፣ ሚዳቋ፣ ነብር፣
ከርከሮ፣ ሰስ፣ ቀበሮ፣ ጅብ፣ እባብ፣ ዘንዶ... የሚርመሰመሱበት የቀለጠ
ዱር ...
የሳለን ተራራ እንደሰንሰለት ተያይዞ ሽቅብ ሲታይ ሰማዩን አቅፎና ደግፎ ያቆመው ሲመስል ኛሮ ደግሞ የታችኛው የቆላው አገረ ገዥነቱን ያለተቀናቃኝ ይዞ ተንሰራፍቷል። የተማመነበትን ሙጥኝ ያለበትን ሽሽቶ የተደበቀበትን አሳልፎ እንደማይሰጥ በኩራት ደረቱን ነፍቶ የሚመሰክር ዱር..
ኛሮ ዳገቱ ላይ ቡልቅ እያለ ከመሬት ውስጥ የሚወጣው የእሳተ ገሞራው
ሲስ በአካባቢው አጠራር “አርቱ” ይባላል። መሬቱ ማስ፣ ማስ ይደረግና ጉድጓድ ከተበጀ በኋላ የጉድጓዱ አፍ በጋቢ ወይንም በቁርበት ይሽፈናል። ከዚያ ምን ያስፈልጋል? ከውስጡ ቁጭ ማለት ነው።በዚያ ትኩስ እሳተ ገሞራ ጢስ እየተቀቀሉ እንደ ቅቤ ሲቀልጡ እንደ ዥረት የሚንቆረቆረው ላብ ቆሻሻውን ሙልጭ አድርጎ ይዞት ይወጣል። በዘመናዊ አጠራር “ሳውና ባዝ እንደሚባለው መሆኑ ነው። ኛሮ ለቤተሰብ አባሎቹ ለተለያዩ የዱር አራዊቶች ገነት ነው፡፡ እንደ ፍላጎታቸው ሁሉንም ችሎ
አቻችሎ ይዟቸዋል፡፡ የሚጋጥ ሳር ለሚጠይቀው ከጨሌው ጀምሮ የሰው
አንገት እስከሚውጠው ሰንበሌጥ ድረስ አብቅሎለታል። ሥጋ ለሚፈልገው በውስጡ ያቀፋቸው ሳር በል አራዊቶች በሽበሽ ስለሆኑ አድፍጦ ጉብ ማለት ብቻ ነው የሚያስፈልገው እንጂ በኛሮ በኩል የተጓደለ ነገር የለም፡፡ ኛሮ የገባን ፈልጎ ማግኘት ቀይ ባህር ውስጥ የወደቀ ቀለበት ለማግኘት እንደመፈለግ ሆኖ ዋሻነቱ ይጋነንለታል፡፡
ፀሀይዋ ደማቅ ጨረሯን በመለገሷ ሙቀቷን ለመቋደስ የሚፈልጉ አራዊ
ቶች ከየዋሻው፣ ከየጢሻውና ከየድንጋዩ ውስጥ እየወጡ ብቅ ብቅ ማለት
ጀምረዋል። ከእነዚህ መካከል ኛሮ በአይነቱም ሆነ በአፈጣጠሩ ለየት
ያለውን በሁለት እግሩ ቆሞ የሚራመደውን አውሬ ከነጀሌዎቹ በቤተሰብ አባልነት ከመዘገባቸው ውሎ አድሯል። ጎንቻ ዘረፋውን በስውር በሌሊት ያከናውንና ወደ ሐሮ ጫካ ተመልሶ ይሰምጣል። ከተራ ሌብነት በደረጃ ዕድገት ሽፍታ ተብሏል፡፡
“ጎንቻ! ጎንቻ ጎንቻ” በበርካታ ሰዎች
አንደበት በፍርሃት የሚጠራ ገናና ስም ሆኗል። በድንገት እየተከስተ መአተ ቁጣውን ካወረደው በኋላ በፍጥነት ስለሚሰወር ስሙ ሲጠራ በፍርሃት የሚርበደበዱና ብርክ የሚይዛቸው ሰዎች ቁጥር እየበራከተ ሄዷል። የጎንቻ ስም ሲጠራ ወንዱ ሱሪው ሊከዳው ይዳዳዋል፡፡ ሴቱ ደግሞ “የጎንቻ አምላክ” ብሎ በፍርሀት ያመልክበት ጀምሯል፡፡ በዚህ ሁኔታ የጎንቻ ዝና ከዳር እስከ ዳር አስተጋባ፡፡ ያንን አስከፊ ወንጀል እያፋፋመው ሲሄድ በቸልታ የተመለከተው ሁሉ ቀስ በቀስ በመቅሰፍት ጅራፉ
እየተሸነቆጠ ነው፡፡ የሌላው ህመም ያልተሰማው “እኔ እስካልተነካሁ ድረስ ምን አገባኝ?” በሚል መንፈስ ተሸብቦ የኖረው ሁሉ ከባድ ችግር ውስጥ እየወደቀ መጥቷል። ገና በእንጭጩ በቁጥጥር ስር ማዋል ሲቻል ጎንቻን የቂም መበቀያ ለማድረግ የሁለት፣የሶስት፣ የአስርና የሃያ ዓመት ቂም እየፈለጉ “እገሌ በሙግት ከመሬቴ ከእርስቴ ነቅሎኛልና ንቀልልኝ ቢቻል በራሱ ላይ ባይቻል በንብረቱ፣ በልጆቹ፣ ወይንም ደግሞ በሚስቱ ላይ አደጋ ጣልልኝ፣ እገሌ በህዝብ ፊት ሰድቦ አዋርዶኛልና አዋርድልኝ።
ይህን ያክል ዋጋ እከፍልሃለሁ” የሚሉ አማላጅ የሚልኩ ስዎች እየበዙ
መጡና በትዕቢት ልቡን አሳበጡት። ጎንቻም በድርድር ገንዘብ እየተቀበለ ፍላጎታቸውን ለማሳካት ባደረገው ጥረት የብዙዎችን አንጀት አራሰ፡፡
አሁን ጎንቻ የዋሻውን ኑሮ እጅግ እየተላመደው መጥቷል። ከሰው ይልቅ
የአራዊት ጠረን ተዋህዶታል፡፡ ከሞቀ ቤት፣ ከሞቀ አልጋ ይልቅ አስፈሪውን ጨለማ፣ዋሻና ጢሻውን የሚመርጥ ሆኗል። ለሰው ልጅ ህይወት ያለው ግምት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ሄዶ የወፍ ያክል እንኳ ዋጋ ሊሰጠው አልቻለም፡፡ ምንም ቢሆን ግን ከአውሬነት ባህሪው ውስጥ ሰው የመሆን ፍጥረቱ ሙሉ ለሙሉ አልጠፋም ነበረና ዘወትር ዓለሚቱን ያስ
ታውሳታል፡፡ ዘወትር ዓለሚቱን ይራባል፡፡ ይናፍቃታል፡፡ ኛሮ ዋሻ ከገባ በኋላ አንድ ሁለት ጊዜ ጨለማን ተገን አድርጎና ራሱን ለውጦ ጎብኝቷታል፡፡ ይሄ ግን ለሱ በቂ አልነበረም፡፡ ምኞቱና ፍላጎቱ ምንግዜም ከአጠገቡ እንዳትለየው አብራው ጫካ እንድትኖር ነው። እሱ የጫካው ንጉሥ
እሷ ደግሞ ንግስት ሆና ያለ አዛዥ ያለተቆጣጣሪ እያዘዙ እየተቆጣጠሩ
እየነጠቀ እየቀማ በድሎት አብሯት መኖር ይፈልጋል። እንደፈለገው እየበላ እየጠጣ ጥጋብ ሲያንጠራራው፣ እንደ ተዋጊ ኮርማ እያነጠነጠ የወሲብ ፍላጎቱ ሲቀሰቀስ የዓለሚቱ ገላ አእምሮውን እስከሚስት ድረስ በዐይኑ ላይ ይሄድበታል...
በኛሮ ጫካ ውስጥ በጎኑ ጋደም ብሎ፣ ጎፈሬውን ወደ ፊትና ወደ ኋላ
አመሳቅሎ፣ ጠመንጃውን እንደሚሰስቱለት ህፃን ልጅ በደረቱ ሸጉጦ የጠዋቷን ፀሀይ ሙቀት በመጋራት ስለሚያከናውናቸው ተግባራት እቅድ
ያወጣል፣ ያወርዳል። የመልኩ ጥቁረት አይነሳ! ከጥቁር አዝሙድ ጋር ይቀራረባል፡፡ ቁመቱ ረዥም ነው፡፡ ጎንቻ! ጎንቻ!! ጎንቻ! የፍርሀት ጌታ!!... የሰቀቀን አምላክ! በበርካታ ህዝብ አንደበት የሚነገረው ዝናው ሰው መሆኑን እንዲጠራጠር አድርጎታል። “ቀላል እና ከባድ ዘረፋን በመለየት ቀላሉን የዘረፋ ትርዒት የሚንቅ ከባዱን የሚወድ፣ ፈታኝ በሆነ ዘረፋና ግድያ የሚረካ በጥቃቅን
ዘረፋና ሌብነት ላይ እጁን የማያስገባ ዝናው የተፈራ ሽፍታ ሆኖ ለመኖር
ራሱን አሳምኗል፡፡ ከኛሮ አልፎ ግዛቱን ወደ ሌላ አስፋፍቶ፣ ጀሌዎቹን
በእጥፍ ድርብ አበራክቶ ዘረፋውን በማጧጧፍ ሀብታም መሆንን እየተመኘ ነው።
ይሄ ምኞቱ እንደሚሳካ ደግሞ ጥርጥር አልነበረውም፡፡ በተለይ ሰሞኑን
መልእክት የላከበት ባላባት ምን ያክል ለቁም ነገር ተፈላጊ ሰው እየሆነ
መምጣቱን አረጋግጦለታል። ወላጅ አባቱ በቶላ ሞት ምክንያት ተበሳጭተው ራሳቸውን በራሳቸው ያጠፉ መሆናቸውን ከጀሌዎቹ አንደበት በሰማበት ዕለት የቀለደው ቀልድ ጀሌዎቹን ጭምር ያስደነገጠ ነበር። ተበድሮ
ያልመለሰለትን ገንዘብ ሊቀበለው ነው አብሮት የሄደው ከተቀበለው በኋላ
ተመልሶ ይመጣልና አታስቡ በማለት ሊያረጋጋቸው መሞከሩ አለቃቸው
ምን ያክል ጨካኝ ሰው እንደሆነ አረጋግጦላቸዋል። ጎንቻ በደም ስሩ
ውስጥ የሚዘዋወረው የወንጀል ዕፅ የመረዘው መራራ ደም ነበረና የባላባቱን ነገር ሲያብሰለስል ከቆየ በኋላ በአፋጣኝ ሄዶ ማንነቱን ሊያስመስ ክር ፈለገ፡፡ ከዚያም ወደ ጀሌዎቹ ዘወር አለና በደፈረሱት ዐይኖቹ አካባቢውን በመቃኘት ጊርቦን አናገረው፡፡
“ስማ ጊርቦ! የሽማግሌው ጉዳይ?!” አለው፡፡ ጊርቦ አለቃው ጎንቻን በጣም የሚያከብር የሚፈራም ሰው ነው፡፡ በተዘረፈ ንብረት ተሸካሚነትና በወንጀል ተባባሪነት ብቻ ሳይሆን ጠቃሚ መረጃዎችን በመስብስብ በኩል ለጎንቻ ቀኝ እጁ ነው፡፡
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...አስቻለው ከተንጋለለበት ብድግ ብሎ ሔዋን ሳማት እሷም ሳመችው። ግን ደግሞ ሁለቱም ሆዳቸው ባባና ተላቀሱ።
ቀጣዬቹ ቀናት የአስቻለው የጉዞ ዝግጅት ጊዜ ሆኑ። ከሁለቱ በፊት የደምወዙን ውክልና ለበልሁ ሰጠ። ቀጥሎም ሔዋንና ትርፌን አስቀምጦበት የሚሄደው ቤት ከግለሰብ የተከራየው በመሆኑ እሱ በሌለበት ችግር እንዴይፈጠርባየው ከባለቤቱ ጋር የቃልም ሆነ የፅሁፍ ውል ማሰር ነበረበትና ጥረቱን ጀመረ።
የቤቱ ባለቤት አቶ ከድር አህመድ በቀበሌ ዜሮ ሰባት ውስጥ የኖራሉ።የሚኖሩበት ቤት ከመጥበቧ የተነሳ ከአንድ ፍራሽ የተረፈችው የሳሎን ቦታ ሌላ
ፍራሽ አታዘረጋም ከጫት መቃምያ ፍራሻቸው ፊት ለፊት ሁለት ወይም ሶስት የዱካ መቀመጫዎች ብቻ ተደርድረዋል። አስቻለውና ሔዋን በተወያዩ በሁለተኛው ቀን ከምሽቱ አስራ አንድ ሰአት አካባቢ አስቻለውና በልሁ አብረው ሄዱ ከአቶ ከድር ቤት ሲገቡ ከባለቤታቸው ጋር ፍራሽ ላይ ጎን ለጎን ቁጭ ብለው ጫት ሲቅሙ አገኛቸው።
«ምን እግር ጣላችሁ ዛሬ ልጆች?» ሲሉ አቶ ከድር አስቻለውና በልሁን ጠየቋቸው።አቶ ከድር በጣም ጥቀር ከመሆናቸው የተነሳ ነጭ ጥርሳቸውን ገለጥ ሲያደርጉት
የሰው ዝጉርጉር መስለው ይታያሉ፡፡ በዚያ ላይ ሰፌድ የሚያህል የእይታ መነጽራቸው ግማሽ ፊታቸውን ሸፍኖት ሲታዩ ሁኔታቸው ያስፈራራል። እድሜአቸው ወደ ሰባ ዓመት የሚጠጋ ሲሆን ሰውነታቸውም መጨማደድ ጀምሯል።
«ስለ ቤት ጉዳይ ላነጋግርዎት ነበር፡፡» አላቸው አስቻለው ከፊት ለፊታቸው ባለች ዱካ ላይ ከበልሁ ጎን ተቀምጦ፡፡
«ልትለቅ ነው?»
“አይ! አይደለም፡፡»
«እንግድያማ ኪራይ ልትጨምር ማሰብህን ልትነግረኝ ነው የመጣኸው ሲሉ አቶ ከድር ቀለዱ፡፡ ጎንበስ ብለው ፈገግ በማለት ጫት ይቀነጣጥባሎ፡፡
«ቢሆንስ ምን ችግር አለው?» አለ አስቻለው በፈገግታ እየተመለከታቸወ፡፡
«ጎሽ የኔ ምሁር አፍክን በዳቦ»
በዚህ ጊዜ ባለቤታቸው ወይዘሮ ሰሚራ አሊ ጭምር በቢቱ ውስጥ ያሉት በሙሉ ሳቁ፡፡
«ለአንድ ስድስት ወር ያህል ወደ ሌላ አገር በጊዜያዊነት ልሄድ ስለሆነ ቤቴ ውስጥ አስቀምጫቸው ስለምሄደው ሰዎች ጉዳይ እንድንጋገር ብዬ ነው የመጣሁት አላቸው አስቻለው ወደ ቁም ነገሩ በመመለስ፡፡
የት ልትሄድ ነው!»
ወደ ኤርትራ ነው ፤ ዘመቻ!»
«አኪምነቱን ትተህ ወታደር ሆንክ እንዴ?» እሉ አቶ ከድር በዚያ
መነፅራቸው ውስጥ ቀና ብለው እያዩት። አስቻለው የአስተሳሰባቸው ከቅጣጫ እንደ
መገረም ብሎት በልሁን እያየ ፈገግ ካለ በኋላ፡-
«አይ ለሌላ ሥራ ነው::» አላቸው፡፡
«ወደዚያ የሚኬደው ለጦርነት ስለሆነ ብዬ ነዋ» ካሎት በኋላ «ታዲያ ማንን ልታስቀምጥበት ፈለግህ?» ሲሉ ጠየቁት፡፡
«ሰራተኛዬንና እጮኛዬን!»
«ሁለቱም ሴቶች ?»
«አዎ» አለና አስቻለው ወደበልሁ እያመለከተ «ይሄ ወንድሜ የቤት ኪራዩን እቤቶ ድረስ እያመጣ ይከፍሎታል።»
«አዬ..» አሉና እንደማቅማማት አሉ። ወደ ባለቤታቸው ዞር በማለት «ይኸን ነገር እንዴት ታይዋለሽ ሰሚራን» ሲሉ ጠየቋቸው፡፡ እርጅና ወደቅ ያለባቸው ቀይ ፋታቸው ጨምደድ ማለት የጀመረው ወይዘሮ ሰሚራ ሙሉ ሰውነታቸውን በሰፊና ረጅም ቀሚሳቸው ሸፍነው በቀይና ነጭ ቡራቡሬ ጉፍታ አንገትና ጭቅላታቸውን ተከናንበው በመቀመጥ ጫት ይቅማሉ። ጀበናና የሲና ረከቦት ከፊታቸው ደርድረዋል።
«እኔ ደሞ ምን አውቄ!» አሏቸው አቶ ከድርን ማየት ከፊታቸው
ያለውን ከሰል እሳት ቆሰቆስ እረጉት፡፡
«ችግር እኮ የለውም አባ አድር!» አላቸው አስቻለው የባልና ሚስቱ
ምልልስ ትንሽም ቢሆን ወደ ስጋት ስሜት ወሰድ አደረገውና ለማስተማመን::
«ስማ የኔ ልጅ!» አሉ አቶ ከድር አጎንብሰው “ጫታቸውን እየቀነጣጠቡ።
«አቤት»
«የሴት ነገር ያው የሴት ነው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ አንተ የምትሄደው ወደ ጦር ሜዳ ነው።
ድንገት መጃለፍም ሊኖር ይችላል። በመሀል ታድያ ችግር የተፈጠረ እንደሆነ ሰዶ ማሳደድ አይሆንም ብለህ ነው?» ሲሉ ጥያቄ አዘል አስተያየት ሰጡና ቀና ብለው ተመለከቱት፡፡
በዚህ ጊዜ በልሁ ንድድ ብሎት በሆዱ ምን ዓይነት ፈልፈላ ሽማግሌ ነው አለና « የሆነው ቢሆን በእርስዎ ቤት ላይ ምን ይመጣል ብለው ፈሩ፣» ሲል ኮስቴር ብሎ ጠየቃቸው፡፡
«አይደለም! አይደለም! መፍራት ጥሩ ነው። ባይሆን ሰሞኑን ከሰሚራ ጋር ተነጋግረን የደረሰበትን ሁኔታ እንገልጥላችሁ
እንዲሆን እንጂ…» ብለው ነገራቸውን ጎተት ሲያደርጉት በልሁ ድንገት ከተቀመጠበት ብድግ አለና፡
«ቢቃ ጌታዬ! ምንም አያስፈልግም፣ ነገ መጥተው ቤትዎን ይረከቡ፡፡» አለና
ወደ እስቻለው ዞር ብሎ «ተነስ እንሂድ!» ብሎት ቀድሞ ከቤት ወጣ::
አስቻለው በአቶ ከድር ሁኔታ ሆዱ እየበሽቀ ነገር ግን በልሁ ምን አስቦ እንደሆነ ግራ እየገባው ብድግ ብሎ ተከተለው፡፡ ከደረሰበትም በኋላ ምንም የተለየ
አማራጭ አልነገረውም። ብቻ «ና ወደ ታፈሡ ጋ ሄደን በጋራ እንነጋገርበታለን::»
ብሎት ሁለቱም ዝም ብለው ወደ ታፈሡ ቤት አመሩ፡፡ በልሁ ገና ሔዋን ከሸዋዬ ቤት መውጣት እንዳለባት ሀሳብ ከቀረበ ጀምሮ
ምናልባት እሺ ብላ ከወጣች በማለት ስለምትኖርበት ቤት አንድ ነገር ሲያሰላስል ቆይቷል። በእሱ እምነት የሸዋዬና የአስቻለው ቤት ተቀራራቢ በመሆኑ ሽዋዬ ነጋ
መሽ እየተመላለሰች ሰላም ልትነሳት ትችላለች። የእሱ ቤት ደግሞ በዜሮ ሁለት ቀበሌ ውስጥ ለዚያውም ዙሪያው በግንብ የታጠረና የተከበረ የትልቅ ሰው ግቢ ነው:: ለርቀቱም ለፀጥታውም ምቹ ስለሆነ ሔዋንን ከትርፌ ጋር እዚያ አስገብቶ
እሱ በአስቻለው ቤት ውስጥ የመኖር ሀሳብ ነበረው። አቶ ከድር ግን እቅዱን አበላሹበት።
በልሁ ይሄንኑ እያሰበ ከአስቻለው ጋ ተጉዞ ከታፈሡ ቤት ደረሱ ሁለቱም ገብተው ከታፈሡ ጋር ቁጭ ሲሉ በልሁ አንድ ነገርም ብቻ ለሁለቱም ነገራቸው።
«ስለ ቤት ጉዳይ ምንም አታስቡ፡፡ ቢቻል ነገ ካልሆነ ግን ከነገ ወዲያ
ሔዋን ጓዟን ጠቅልላ ከሸዋዬ ቤት የምትወጣበትን ሁኔታ ብቻ አስቡ፡፡ ሌላውን ነገር ለኔ ተውት አላቸው።
የሆነውም ይኸው ነበር፡፡ በልሁ ያንዕትን ልብሶችና የመጽሐፍ መደርደሪያ ይዞ ከአንድ ሆቴል ውስጥ ኮንትራት አልጋ ይዞ ገባ፡፡ ሔዋንም እንኳንስ ጫማ እና ልብሶቿ!! የአለቀ የእስክሪብቶ ቀፎ እንኳ ሳይቀራት ጓዟን ጠቅልላ በሚቀጥለው ቀን ወደ ታፈሡ ቤት መጣች፡፡ ያ ቀን ማግስት ምሽት ላይ ደግሞ ከትርፌ ጋር በበልሁ ቤት ውስጥ 'ቤት ለንሞባሳ ብለው ገቡ።
የዚያኑ ዕለት ለአስቻለው አጠር ያለ ሽኝት ተዘጋጀ። አዎ! ለነገሩ ጥሩ ምግብ ተበላ መጠጦች በያይነቱ ተጠጡ።። ነገር ግን መስፈሪያ ኖሮት የሚለካ ቢሆን ኖሮ በሽኝቱ እለት ሲወርድ ያመሸው እንባ ምን ያህል ከመያዣው ተርፎ በፈሰሰ ነበር፡፡ ሔዋን በሰቀቀን "እየዮ” ስትል አስቻለው በቁጭት "እህህ" ሲል
አፆናኝና ጋባዦቹ ታፈሡ በልዑና መርዕድም ከእጃቸው ላይ መሀረብ ሳይለይ ሌሊቱ ወለል ብሎ ነጋ።
አስቻለው በጠዋት በማለዳ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ዋለና በሶስተኛው ቀን ቀትር ላይ ደግሞ በአይሮፕላን ወደ አስመራ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...አስቻለው ከተንጋለለበት ብድግ ብሎ ሔዋን ሳማት እሷም ሳመችው። ግን ደግሞ ሁለቱም ሆዳቸው ባባና ተላቀሱ።
ቀጣዬቹ ቀናት የአስቻለው የጉዞ ዝግጅት ጊዜ ሆኑ። ከሁለቱ በፊት የደምወዙን ውክልና ለበልሁ ሰጠ። ቀጥሎም ሔዋንና ትርፌን አስቀምጦበት የሚሄደው ቤት ከግለሰብ የተከራየው በመሆኑ እሱ በሌለበት ችግር እንዴይፈጠርባየው ከባለቤቱ ጋር የቃልም ሆነ የፅሁፍ ውል ማሰር ነበረበትና ጥረቱን ጀመረ።
የቤቱ ባለቤት አቶ ከድር አህመድ በቀበሌ ዜሮ ሰባት ውስጥ የኖራሉ።የሚኖሩበት ቤት ከመጥበቧ የተነሳ ከአንድ ፍራሽ የተረፈችው የሳሎን ቦታ ሌላ
ፍራሽ አታዘረጋም ከጫት መቃምያ ፍራሻቸው ፊት ለፊት ሁለት ወይም ሶስት የዱካ መቀመጫዎች ብቻ ተደርድረዋል። አስቻለውና ሔዋን በተወያዩ በሁለተኛው ቀን ከምሽቱ አስራ አንድ ሰአት አካባቢ አስቻለውና በልሁ አብረው ሄዱ ከአቶ ከድር ቤት ሲገቡ ከባለቤታቸው ጋር ፍራሽ ላይ ጎን ለጎን ቁጭ ብለው ጫት ሲቅሙ አገኛቸው።
«ምን እግር ጣላችሁ ዛሬ ልጆች?» ሲሉ አቶ ከድር አስቻለውና በልሁን ጠየቋቸው።አቶ ከድር በጣም ጥቀር ከመሆናቸው የተነሳ ነጭ ጥርሳቸውን ገለጥ ሲያደርጉት
የሰው ዝጉርጉር መስለው ይታያሉ፡፡ በዚያ ላይ ሰፌድ የሚያህል የእይታ መነጽራቸው ግማሽ ፊታቸውን ሸፍኖት ሲታዩ ሁኔታቸው ያስፈራራል። እድሜአቸው ወደ ሰባ ዓመት የሚጠጋ ሲሆን ሰውነታቸውም መጨማደድ ጀምሯል።
«ስለ ቤት ጉዳይ ላነጋግርዎት ነበር፡፡» አላቸው አስቻለው ከፊት ለፊታቸው ባለች ዱካ ላይ ከበልሁ ጎን ተቀምጦ፡፡
«ልትለቅ ነው?»
“አይ! አይደለም፡፡»
«እንግድያማ ኪራይ ልትጨምር ማሰብህን ልትነግረኝ ነው የመጣኸው ሲሉ አቶ ከድር ቀለዱ፡፡ ጎንበስ ብለው ፈገግ በማለት ጫት ይቀነጣጥባሎ፡፡
«ቢሆንስ ምን ችግር አለው?» አለ አስቻለው በፈገግታ እየተመለከታቸወ፡፡
«ጎሽ የኔ ምሁር አፍክን በዳቦ»
በዚህ ጊዜ ባለቤታቸው ወይዘሮ ሰሚራ አሊ ጭምር በቢቱ ውስጥ ያሉት በሙሉ ሳቁ፡፡
«ለአንድ ስድስት ወር ያህል ወደ ሌላ አገር በጊዜያዊነት ልሄድ ስለሆነ ቤቴ ውስጥ አስቀምጫቸው ስለምሄደው ሰዎች ጉዳይ እንድንጋገር ብዬ ነው የመጣሁት አላቸው አስቻለው ወደ ቁም ነገሩ በመመለስ፡፡
የት ልትሄድ ነው!»
ወደ ኤርትራ ነው ፤ ዘመቻ!»
«አኪምነቱን ትተህ ወታደር ሆንክ እንዴ?» እሉ አቶ ከድር በዚያ
መነፅራቸው ውስጥ ቀና ብለው እያዩት። አስቻለው የአስተሳሰባቸው ከቅጣጫ እንደ
መገረም ብሎት በልሁን እያየ ፈገግ ካለ በኋላ፡-
«አይ ለሌላ ሥራ ነው::» አላቸው፡፡
«ወደዚያ የሚኬደው ለጦርነት ስለሆነ ብዬ ነዋ» ካሎት በኋላ «ታዲያ ማንን ልታስቀምጥበት ፈለግህ?» ሲሉ ጠየቁት፡፡
«ሰራተኛዬንና እጮኛዬን!»
«ሁለቱም ሴቶች ?»
«አዎ» አለና አስቻለው ወደበልሁ እያመለከተ «ይሄ ወንድሜ የቤት ኪራዩን እቤቶ ድረስ እያመጣ ይከፍሎታል።»
«አዬ..» አሉና እንደማቅማማት አሉ። ወደ ባለቤታቸው ዞር በማለት «ይኸን ነገር እንዴት ታይዋለሽ ሰሚራን» ሲሉ ጠየቋቸው፡፡ እርጅና ወደቅ ያለባቸው ቀይ ፋታቸው ጨምደድ ማለት የጀመረው ወይዘሮ ሰሚራ ሙሉ ሰውነታቸውን በሰፊና ረጅም ቀሚሳቸው ሸፍነው በቀይና ነጭ ቡራቡሬ ጉፍታ አንገትና ጭቅላታቸውን ተከናንበው በመቀመጥ ጫት ይቅማሉ። ጀበናና የሲና ረከቦት ከፊታቸው ደርድረዋል።
«እኔ ደሞ ምን አውቄ!» አሏቸው አቶ ከድርን ማየት ከፊታቸው
ያለውን ከሰል እሳት ቆሰቆስ እረጉት፡፡
«ችግር እኮ የለውም አባ አድር!» አላቸው አስቻለው የባልና ሚስቱ
ምልልስ ትንሽም ቢሆን ወደ ስጋት ስሜት ወሰድ አደረገውና ለማስተማመን::
«ስማ የኔ ልጅ!» አሉ አቶ ከድር አጎንብሰው “ጫታቸውን እየቀነጣጠቡ።
«አቤት»
«የሴት ነገር ያው የሴት ነው፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ አንተ የምትሄደው ወደ ጦር ሜዳ ነው።
ድንገት መጃለፍም ሊኖር ይችላል። በመሀል ታድያ ችግር የተፈጠረ እንደሆነ ሰዶ ማሳደድ አይሆንም ብለህ ነው?» ሲሉ ጥያቄ አዘል አስተያየት ሰጡና ቀና ብለው ተመለከቱት፡፡
በዚህ ጊዜ በልሁ ንድድ ብሎት በሆዱ ምን ዓይነት ፈልፈላ ሽማግሌ ነው አለና « የሆነው ቢሆን በእርስዎ ቤት ላይ ምን ይመጣል ብለው ፈሩ፣» ሲል ኮስቴር ብሎ ጠየቃቸው፡፡
«አይደለም! አይደለም! መፍራት ጥሩ ነው። ባይሆን ሰሞኑን ከሰሚራ ጋር ተነጋግረን የደረሰበትን ሁኔታ እንገልጥላችሁ
እንዲሆን እንጂ…» ብለው ነገራቸውን ጎተት ሲያደርጉት በልሁ ድንገት ከተቀመጠበት ብድግ አለና፡
«ቢቃ ጌታዬ! ምንም አያስፈልግም፣ ነገ መጥተው ቤትዎን ይረከቡ፡፡» አለና
ወደ እስቻለው ዞር ብሎ «ተነስ እንሂድ!» ብሎት ቀድሞ ከቤት ወጣ::
አስቻለው በአቶ ከድር ሁኔታ ሆዱ እየበሽቀ ነገር ግን በልሁ ምን አስቦ እንደሆነ ግራ እየገባው ብድግ ብሎ ተከተለው፡፡ ከደረሰበትም በኋላ ምንም የተለየ
አማራጭ አልነገረውም። ብቻ «ና ወደ ታፈሡ ጋ ሄደን በጋራ እንነጋገርበታለን::»
ብሎት ሁለቱም ዝም ብለው ወደ ታፈሡ ቤት አመሩ፡፡ በልሁ ገና ሔዋን ከሸዋዬ ቤት መውጣት እንዳለባት ሀሳብ ከቀረበ ጀምሮ
ምናልባት እሺ ብላ ከወጣች በማለት ስለምትኖርበት ቤት አንድ ነገር ሲያሰላስል ቆይቷል። በእሱ እምነት የሸዋዬና የአስቻለው ቤት ተቀራራቢ በመሆኑ ሽዋዬ ነጋ
መሽ እየተመላለሰች ሰላም ልትነሳት ትችላለች። የእሱ ቤት ደግሞ በዜሮ ሁለት ቀበሌ ውስጥ ለዚያውም ዙሪያው በግንብ የታጠረና የተከበረ የትልቅ ሰው ግቢ ነው:: ለርቀቱም ለፀጥታውም ምቹ ስለሆነ ሔዋንን ከትርፌ ጋር እዚያ አስገብቶ
እሱ በአስቻለው ቤት ውስጥ የመኖር ሀሳብ ነበረው። አቶ ከድር ግን እቅዱን አበላሹበት።
በልሁ ይሄንኑ እያሰበ ከአስቻለው ጋ ተጉዞ ከታፈሡ ቤት ደረሱ ሁለቱም ገብተው ከታፈሡ ጋር ቁጭ ሲሉ በልሁ አንድ ነገርም ብቻ ለሁለቱም ነገራቸው።
«ስለ ቤት ጉዳይ ምንም አታስቡ፡፡ ቢቻል ነገ ካልሆነ ግን ከነገ ወዲያ
ሔዋን ጓዟን ጠቅልላ ከሸዋዬ ቤት የምትወጣበትን ሁኔታ ብቻ አስቡ፡፡ ሌላውን ነገር ለኔ ተውት አላቸው።
የሆነውም ይኸው ነበር፡፡ በልሁ ያንዕትን ልብሶችና የመጽሐፍ መደርደሪያ ይዞ ከአንድ ሆቴል ውስጥ ኮንትራት አልጋ ይዞ ገባ፡፡ ሔዋንም እንኳንስ ጫማ እና ልብሶቿ!! የአለቀ የእስክሪብቶ ቀፎ እንኳ ሳይቀራት ጓዟን ጠቅልላ በሚቀጥለው ቀን ወደ ታፈሡ ቤት መጣች፡፡ ያ ቀን ማግስት ምሽት ላይ ደግሞ ከትርፌ ጋር በበልሁ ቤት ውስጥ 'ቤት ለንሞባሳ ብለው ገቡ።
የዚያኑ ዕለት ለአስቻለው አጠር ያለ ሽኝት ተዘጋጀ። አዎ! ለነገሩ ጥሩ ምግብ ተበላ መጠጦች በያይነቱ ተጠጡ።። ነገር ግን መስፈሪያ ኖሮት የሚለካ ቢሆን ኖሮ በሽኝቱ እለት ሲወርድ ያመሸው እንባ ምን ያህል ከመያዣው ተርፎ በፈሰሰ ነበር፡፡ ሔዋን በሰቀቀን "እየዮ” ስትል አስቻለው በቁጭት "እህህ" ሲል
አፆናኝና ጋባዦቹ ታፈሡ በልዑና መርዕድም ከእጃቸው ላይ መሀረብ ሳይለይ ሌሊቱ ወለል ብሎ ነጋ።
አስቻለው በጠዋት በማለዳ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ዋለና በሶስተኛው ቀን ቀትር ላይ ደግሞ በአይሮፕላን ወደ አስመራ።
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢያሱን ከሐሳቧ ማውጣት አቃታት። ጭንቅላቷ
ከእሱ ሌላ ማሰብ ተሳነው። ይኸ ሰው እኮ የጃንሆይ እት ልዥ ነው።
እንዴት ሁኖ ነው ኸሱ ጋር ሰውስ ምን ይላል? ይቅርብኝ ይኸ ነገር፡
አግባብ ማዶል። የጃንሆይ አጥንት ይወቅሰኛል። ለስሜም ለልዥም
ክብር ተገቢ ማዶል። ልዝም ቢሆን ሲያድግ ያባቴ ክብር ተነካ
ብሎ መቀየሙ አይቀርም፡፡ አምላኬ ምነው እንደዝኸ ያለ መፈታተኛ ሰጠኸኝ? እያለች አምላኳን ሞገተች።
የራሷን ፍላጎትና የሰዉን አመለካከት ስታወዳድር፣ ስታመዛዝን፣ስትጨነቅ፣ ልቧ ሲማስን ወራት አለፉ። ኢያሱ፣ መጥቶ እንደወትሯቸው
እንዳይጫወቱ ምክንያት እየሰጠች ከቤተመንግሥት እንዲርቅ አደረገችው። ውስጧ ለሚንቀለቀለውም ስሜት ልጓም ልታበጅለት ፈለገች። ኅሊናዋ አንዴ ሲከሳት፣ ሌላ ጊዜ ሲፈርድባት፣ አንቺ የቁስቋሟ፡
ይኸን ነገር ኸልቤ አውጭልኝ እያለች ማርያምን ተማፀነች።
ልቧ ግን ወደ እሱ አዘነበለ። የፍቅርን ዕርከን እያዘገመ ወጣ። እንደ እምቡጥ ጽጌሬዳ ራሱ የፈነዳና የአበበ ንፁህ ፍቅር በውስጡ ሰረፀ። በሠራ አካላቷ ተበተነ፣ ዐዲስ ሕይወት በመላ ሰውነቷ ውስጥ አንሰራራ፣
የጎደለው ልቧ ሞላ።
ኢያሱም ቢሆን አጎቱ ከሞቱ በኋላ፣ ቤተመንግሥት አዘውትሮ
መምጣቱ አለነገሩ እንዳልሆነ ገባት። የእሱም ልብ መዋለሉን ተረዳች።ከሰው መሀል ዝምታው ሲያነጋግራት፣ ዐይኖቿ የፍቅር ግብር ሲልኩ፣ገፅታው ጥያቄዎቿን ሲመልስላት ልቧ ከልቡ እንደተጣመረ አወቀች።
ኅሊናዋ መሞገቱን ተወ። ጭራሽ ገፋፋት፤ አሻፈረኝ፣ ባህልና ሥርዐት አያግደኝ በይ አላት።
የወደደ የተሸሽገን አያጣውም እንዲሉ፣ ኢያሱን ለብቻው እልፍኟ
ማስጠራት ጀመረች። ሲመጣ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ማውራትና
መጫወት ትፈልጋለች። ዘውዷን አውርዳ፣ ካባዋን ወርውራ፣ እቴጌ
ሳትሆን ሰው ሆና ትጠብቀዋለች።
መስተዋት ፊት ስትቆም፣ ዕድሜ አካሏ ላይ ያመጣውን ለውጥ
ለመፈተሽ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ ያቺ ቋራን ስትለቅ ዐዲስ የፈነዳ አበባ የመሰለችው ወጣት ዛሬ ዕድሜ ሰውነቷን ሞልቶ፣ አካሏንና አእምሮዋን አዳብሮ በውበት ላይ ውበት አክሎላት ገና የደረሰ ፍሬ መምሰሏ አልታወቅ ይላታል። ግንባሯን ፈታ፣ ጨምደድ አድርጋ፣ ወደ መስተዋቱ ጠጋ፣ ራቅ ስትል ያሉትም የሌሉትም መስመሮች ይታይዋታል። እህል በልቶ የሚያውቅ የማይመስለውን ወገቧን ወደ ጎን፣ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እያለች ትመለከትና ያች የቋራዋ ጉብል ኣልመስል ትላታለች፡፡
ያን ሰዐት ግዝየ ሌባ ነው ትላለች።
ኢያሱን ለብቻው ማግኘት ስትጀምር፣ ወሬው ከቤተመንግሥት ባለሟሎች ሹክሹክታ አልፎ መሣፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ካህናቱ፣ ሊቃውንቱና
ወይዛዝርቱ መሃል፣ ብሎም ሕዝቡጋ ደረሰ፤ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር ወዳጅነት ያዙ” እየተባለ ተናፈሰ።
ምንትዋብ ግን ወሬውን ከቁብም አልቆጠረችው።
ጭራሹን ከኢያሱ ጋር በድብቅ ተጋቡ። ጐንደሬዎች “ምልምል
የሚል ቅጽል ስም... የተመረጠው ለማለት... አወጡለት። ምንትዋብ
ምልምል እንዳይሉት ግራዝማች አለችው። ግራዝማች ኢያሱ የሰጣትን ዐዲስ የተገኘ ነፃነት ወደደችው። በልጅነቷ ቤተመንግሥት ገብታ ሕይወቷ በወግ ታጥሮ ቆይቶ አሁን እንደ ተራ ሰው መወደድ እናት መወደድ መቻሏ ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ሰጠው።
አንድ ቀን ግን ይህንን ትርጉም የሚገዳደር፣ ነፃነቷን የሚያውክ ነገር ተፈጠረ። ጠዋት ላይ እልፍኟ ተቀምጣ በሐሳብ ዥው ብላለች፤ ከፊሉን ጊዜ ስለ ኢያሱ፣ ከፊሉን ጊዜ ደግሞ ስለ ግብር አዳራሽ ግንባታ ታስባለች።
ዋና የእልፍኝ አስከልካዩ አርከኤድስ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና፣ “አንድ መነኩሴ ኸነማይ መልክት ይዤ መጥቻለሁ ብለው በር ላይ ናቸው።
የውጭ በር ላይ አላስገባ ብለዋቸው መመላለሳቸውን ብሰማ፣ ግቢ እንዲገቡ አርጌ አነጋገርኳቸው። 'ስመላለስ ከረምሁ፣ ብዙም ተጉላላሁ።
አገሬ መመለሻ ግዝየ በመጉላላት አለፈ። ለእቴጌ በእጅ ስጥ ተብየ
ይዤ የመጣሁትን መልክት እንዴት አድርጌ ይዤ መለሳለሁ እያልሁ
ኸዝሁ ከረምሁ እያሉ ቢጨነቁ ይጠብቁ ብያቸው መጣሁ” አላት።
“ኸነማይ?” አለች፣ ምንትዋብ ተገርማ። ከነማይ ማን መልዕክት
ሊልክላት እንዲሚችል መገመት አቅቷት።
“አዎ... ዘመድ ልኮኝ ነው አሉ። የተጠቀለለ ነገር ይዘዋል። “ለእቴጌ በጃቸው በቀር ለሌላ እንዳትሰጥ ብለው አስምለውኝ ነው ያመጣሁት ይላሉ።”
የማናቸው መነኩሴ? እያለች ትንሽ ካሰበች በኋላ፣ “ይግቡ!" አለችው።
አዛዥ አርከሌድስ እጅ ነስቶ ወጣ። ጥቂት ቆይቶ በእሱ መሪነት
ቆብ የደፉ፣ ረጅምና ሰፊ ቀሚስ ያጠለቁ፣ ሽማግሌ ሰው ገብተው
መሬት ሊስሙ ሲያጎነብሱ፣ “ግድ የለም አባቴ ይቀመጡ” አለቻቸው፣ ምንትዋብ።
ፈንጠር ብለው ወንበር ላይ ተቀመጡ።
“አባቴ ኸየት መጡ? ደሞስ ማን ልኮዎት ነው የመጡ?” አለቻቸው። መነኩሴው ከተቀመጡበት ተነሥተው ለጥ ብለው እጅ ነሱ። “እቴጌ ዝናዎን ስሰማ ቆይቸ ዛሬ እርሶን ለማየት ያበቃችኝ ኪዳነ ምረት
ምስጋና ይግባት። እቴጌ ኸነማይ ነው የመጣሁ። ደፈጫ ኪዳነ ምረት ስለት ነበረኝና እሱን ላደርስ መኸዴ ነው ብየ ስነሳ አንድ ኸኛ ዘንድ ሚመላለሱ ሰው፣ '
እኼን ለእቴጌ እንደምንም ብለው አድርሱልኝ። ዐደራ በእጅ ይስጡልኝ። ዘመድ ነኝ ቢሉኝ አመንኳቸው።”
“ሰውየው ማን ይባለሉ?”
“እቴጌ ዕቃውን ሲያዩ ማን እንደሆንሁ ያቃሉ ብለውኛል” ብለው ጥቅሉን አሳዩ።
ምንትዋብ፣ አርከሌድስን፣ “ተቀበልና ፍታው” አለችው።
“እቴጌ ኸርሶ በቀር ለሌላ አትስጥ ተብያለሁ” አሉ፣ መነኩሴው፣
ብድግ ብለው።
“ይቀመጡ... ይስጡትና እኔ ፈታዋለሁ።”
ጥቅሉን ለአርከሌድስ ሲሰጡት ተቀብላ ስትፈታው ዐራት ማዕዘን
እንጨት ላይ የተሣለ የራሷ ምስል ነው። ነጠላ ተከናንባ ወፍታ ጊዮርጊስ ደጀሰላም ላይ ነው። መብረቅ የመታት ያህል ክው ብላ ቀረች።
መነኩሴው የፊቷን መለዋወጥ አይተው ደነገጡ። ከተቀመጡበት
ተነሱ። “እቴጌ... ክፉ ነገር ኑሯል?” ሲሉ ጠየቋት።
የለ፣ ደግ ነው። ብቻ ያልጠበቅሁት ነገር ሁኖብኝ ነው። የላክሁ
ሰውየ ስማቸው ማነው ነበር ያሉኝ?”.
ስማቸውን ስንኳ አላወቅሁም። እኔ ብዙ ግዝየን ኸሰው ስለማልገናኝ
ስለሰዎች እምብዛም አላውቅም። 'እነማይ ለጉዳይ መጠቼ፣ ጐንደር“
ይኸዳሉ ሲሉ ብሰማ ተላኩኝ ብየ ነው። ለእቴጌም ዘመድ ነኝ። የእቴጌ አያቶች እኮ ትውልዳቸው ኸዝሁ ኸኛው ዘንድ ነው ቢሉኝ ምን ከፋኝ ብየ ይዤ መጣሁ።”
“ወደ እነማይ በቅርቡ ይመለሳሉ?”
“ለርሶ መልክቴን ካደረስሁ እንግዲህ ነገ እነሳለሁ።”
“እንግዲያማ ደሕና ግቡ። ለላኩዎም ሰው ባክዎን ወደ ጐንደር ብቅ ይበሉ። እንደርሶ ያለ ሠዓሊ ፈልጋለሁ ይበሉልኝ” አለቻቸው።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢያሱን ከሐሳቧ ማውጣት አቃታት። ጭንቅላቷ
ከእሱ ሌላ ማሰብ ተሳነው። ይኸ ሰው እኮ የጃንሆይ እት ልዥ ነው።
እንዴት ሁኖ ነው ኸሱ ጋር ሰውስ ምን ይላል? ይቅርብኝ ይኸ ነገር፡
አግባብ ማዶል። የጃንሆይ አጥንት ይወቅሰኛል። ለስሜም ለልዥም
ክብር ተገቢ ማዶል። ልዝም ቢሆን ሲያድግ ያባቴ ክብር ተነካ
ብሎ መቀየሙ አይቀርም፡፡ አምላኬ ምነው እንደዝኸ ያለ መፈታተኛ ሰጠኸኝ? እያለች አምላኳን ሞገተች።
የራሷን ፍላጎትና የሰዉን አመለካከት ስታወዳድር፣ ስታመዛዝን፣ስትጨነቅ፣ ልቧ ሲማስን ወራት አለፉ። ኢያሱ፣ መጥቶ እንደወትሯቸው
እንዳይጫወቱ ምክንያት እየሰጠች ከቤተመንግሥት እንዲርቅ አደረገችው። ውስጧ ለሚንቀለቀለውም ስሜት ልጓም ልታበጅለት ፈለገች። ኅሊናዋ አንዴ ሲከሳት፣ ሌላ ጊዜ ሲፈርድባት፣ አንቺ የቁስቋሟ፡
ይኸን ነገር ኸልቤ አውጭልኝ እያለች ማርያምን ተማፀነች።
ልቧ ግን ወደ እሱ አዘነበለ። የፍቅርን ዕርከን እያዘገመ ወጣ። እንደ እምቡጥ ጽጌሬዳ ራሱ የፈነዳና የአበበ ንፁህ ፍቅር በውስጡ ሰረፀ። በሠራ አካላቷ ተበተነ፣ ዐዲስ ሕይወት በመላ ሰውነቷ ውስጥ አንሰራራ፣
የጎደለው ልቧ ሞላ።
ኢያሱም ቢሆን አጎቱ ከሞቱ በኋላ፣ ቤተመንግሥት አዘውትሮ
መምጣቱ አለነገሩ እንዳልሆነ ገባት። የእሱም ልብ መዋለሉን ተረዳች።ከሰው መሀል ዝምታው ሲያነጋግራት፣ ዐይኖቿ የፍቅር ግብር ሲልኩ፣ገፅታው ጥያቄዎቿን ሲመልስላት ልቧ ከልቡ እንደተጣመረ አወቀች።
ኅሊናዋ መሞገቱን ተወ። ጭራሽ ገፋፋት፤ አሻፈረኝ፣ ባህልና ሥርዐት አያግደኝ በይ አላት።
የወደደ የተሸሽገን አያጣውም እንዲሉ፣ ኢያሱን ለብቻው እልፍኟ
ማስጠራት ጀመረች። ሲመጣ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ማውራትና
መጫወት ትፈልጋለች። ዘውዷን አውርዳ፣ ካባዋን ወርውራ፣ እቴጌ
ሳትሆን ሰው ሆና ትጠብቀዋለች።
መስተዋት ፊት ስትቆም፣ ዕድሜ አካሏ ላይ ያመጣውን ለውጥ
ለመፈተሽ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ ያቺ ቋራን ስትለቅ ዐዲስ የፈነዳ አበባ የመሰለችው ወጣት ዛሬ ዕድሜ ሰውነቷን ሞልቶ፣ አካሏንና አእምሮዋን አዳብሮ በውበት ላይ ውበት አክሎላት ገና የደረሰ ፍሬ መምሰሏ አልታወቅ ይላታል። ግንባሯን ፈታ፣ ጨምደድ አድርጋ፣ ወደ መስተዋቱ ጠጋ፣ ራቅ ስትል ያሉትም የሌሉትም መስመሮች ይታይዋታል። እህል በልቶ የሚያውቅ የማይመስለውን ወገቧን ወደ ጎን፣ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እያለች ትመለከትና ያች የቋራዋ ጉብል ኣልመስል ትላታለች፡፡
ያን ሰዐት ግዝየ ሌባ ነው ትላለች።
ኢያሱን ለብቻው ማግኘት ስትጀምር፣ ወሬው ከቤተመንግሥት ባለሟሎች ሹክሹክታ አልፎ መሣፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ካህናቱ፣ ሊቃውንቱና
ወይዛዝርቱ መሃል፣ ብሎም ሕዝቡጋ ደረሰ፤ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር ወዳጅነት ያዙ” እየተባለ ተናፈሰ።
ምንትዋብ ግን ወሬውን ከቁብም አልቆጠረችው።
ጭራሹን ከኢያሱ ጋር በድብቅ ተጋቡ። ጐንደሬዎች “ምልምል
የሚል ቅጽል ስም... የተመረጠው ለማለት... አወጡለት። ምንትዋብ
ምልምል እንዳይሉት ግራዝማች አለችው። ግራዝማች ኢያሱ የሰጣትን ዐዲስ የተገኘ ነፃነት ወደደችው። በልጅነቷ ቤተመንግሥት ገብታ ሕይወቷ በወግ ታጥሮ ቆይቶ አሁን እንደ ተራ ሰው መወደድ እናት መወደድ መቻሏ ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ሰጠው።
አንድ ቀን ግን ይህንን ትርጉም የሚገዳደር፣ ነፃነቷን የሚያውክ ነገር ተፈጠረ። ጠዋት ላይ እልፍኟ ተቀምጣ በሐሳብ ዥው ብላለች፤ ከፊሉን ጊዜ ስለ ኢያሱ፣ ከፊሉን ጊዜ ደግሞ ስለ ግብር አዳራሽ ግንባታ ታስባለች።
ዋና የእልፍኝ አስከልካዩ አርከኤድስ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና፣ “አንድ መነኩሴ ኸነማይ መልክት ይዤ መጥቻለሁ ብለው በር ላይ ናቸው።
የውጭ በር ላይ አላስገባ ብለዋቸው መመላለሳቸውን ብሰማ፣ ግቢ እንዲገቡ አርጌ አነጋገርኳቸው። 'ስመላለስ ከረምሁ፣ ብዙም ተጉላላሁ።
አገሬ መመለሻ ግዝየ በመጉላላት አለፈ። ለእቴጌ በእጅ ስጥ ተብየ
ይዤ የመጣሁትን መልክት እንዴት አድርጌ ይዤ መለሳለሁ እያልሁ
ኸዝሁ ከረምሁ እያሉ ቢጨነቁ ይጠብቁ ብያቸው መጣሁ” አላት።
“ኸነማይ?” አለች፣ ምንትዋብ ተገርማ። ከነማይ ማን መልዕክት
ሊልክላት እንዲሚችል መገመት አቅቷት።
“አዎ... ዘመድ ልኮኝ ነው አሉ። የተጠቀለለ ነገር ይዘዋል። “ለእቴጌ በጃቸው በቀር ለሌላ እንዳትሰጥ ብለው አስምለውኝ ነው ያመጣሁት ይላሉ።”
የማናቸው መነኩሴ? እያለች ትንሽ ካሰበች በኋላ፣ “ይግቡ!" አለችው።
አዛዥ አርከሌድስ እጅ ነስቶ ወጣ። ጥቂት ቆይቶ በእሱ መሪነት
ቆብ የደፉ፣ ረጅምና ሰፊ ቀሚስ ያጠለቁ፣ ሽማግሌ ሰው ገብተው
መሬት ሊስሙ ሲያጎነብሱ፣ “ግድ የለም አባቴ ይቀመጡ” አለቻቸው፣ ምንትዋብ።
ፈንጠር ብለው ወንበር ላይ ተቀመጡ።
“አባቴ ኸየት መጡ? ደሞስ ማን ልኮዎት ነው የመጡ?” አለቻቸው። መነኩሴው ከተቀመጡበት ተነሥተው ለጥ ብለው እጅ ነሱ። “እቴጌ ዝናዎን ስሰማ ቆይቸ ዛሬ እርሶን ለማየት ያበቃችኝ ኪዳነ ምረት
ምስጋና ይግባት። እቴጌ ኸነማይ ነው የመጣሁ። ደፈጫ ኪዳነ ምረት ስለት ነበረኝና እሱን ላደርስ መኸዴ ነው ብየ ስነሳ አንድ ኸኛ ዘንድ ሚመላለሱ ሰው፣ '
እኼን ለእቴጌ እንደምንም ብለው አድርሱልኝ። ዐደራ በእጅ ይስጡልኝ። ዘመድ ነኝ ቢሉኝ አመንኳቸው።”
“ሰውየው ማን ይባለሉ?”
“እቴጌ ዕቃውን ሲያዩ ማን እንደሆንሁ ያቃሉ ብለውኛል” ብለው ጥቅሉን አሳዩ።
ምንትዋብ፣ አርከሌድስን፣ “ተቀበልና ፍታው” አለችው።
“እቴጌ ኸርሶ በቀር ለሌላ አትስጥ ተብያለሁ” አሉ፣ መነኩሴው፣
ብድግ ብለው።
“ይቀመጡ... ይስጡትና እኔ ፈታዋለሁ።”
ጥቅሉን ለአርከሌድስ ሲሰጡት ተቀብላ ስትፈታው ዐራት ማዕዘን
እንጨት ላይ የተሣለ የራሷ ምስል ነው። ነጠላ ተከናንባ ወፍታ ጊዮርጊስ ደጀሰላም ላይ ነው። መብረቅ የመታት ያህል ክው ብላ ቀረች።
መነኩሴው የፊቷን መለዋወጥ አይተው ደነገጡ። ከተቀመጡበት
ተነሱ። “እቴጌ... ክፉ ነገር ኑሯል?” ሲሉ ጠየቋት።
የለ፣ ደግ ነው። ብቻ ያልጠበቅሁት ነገር ሁኖብኝ ነው። የላክሁ
ሰውየ ስማቸው ማነው ነበር ያሉኝ?”.
ስማቸውን ስንኳ አላወቅሁም። እኔ ብዙ ግዝየን ኸሰው ስለማልገናኝ
ስለሰዎች እምብዛም አላውቅም። 'እነማይ ለጉዳይ መጠቼ፣ ጐንደር“
ይኸዳሉ ሲሉ ብሰማ ተላኩኝ ብየ ነው። ለእቴጌም ዘመድ ነኝ። የእቴጌ አያቶች እኮ ትውልዳቸው ኸዝሁ ኸኛው ዘንድ ነው ቢሉኝ ምን ከፋኝ ብየ ይዤ መጣሁ።”
“ወደ እነማይ በቅርቡ ይመለሳሉ?”
“ለርሶ መልክቴን ካደረስሁ እንግዲህ ነገ እነሳለሁ።”
“እንግዲያማ ደሕና ግቡ። ለላኩዎም ሰው ባክዎን ወደ ጐንደር ብቅ ይበሉ። እንደርሶ ያለ ሠዓሊ ፈልጋለሁ ይበሉልኝ” አለቻቸው።
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
....ከዚህ በፊት መፅሀፌ " እምቢ
ሲለኝ፣ አንተን አባርሬ ምን ነበር የማረገው መሰለህ?»
«ከመፅሀፍሽ ጋር የምትታገዪ ነበር የሚመስለኝ»
ተሳስተሀል። በየቀኑ ከምሳ በኋላ ማርሰይ እወርድና፡ ከሰአት
በኋላውን፣ ማታውን፣ አንድ አራት አምስት ወንድ ተኝቶኝ፣ ወደ
እኩለ ሌሊት ላይ ድክም ብሎኝ ወደ ኤክስ እመለሳለሁ:: በቀን
በቀኑ ይህን አረጋለሁ። አንድ ቀን ልሄድ ስዘጋጅ ፃፊ ፃፊ ይለኛል፡፡
መፃፍ እጀምራለሁ፡፡ ወንዶቹ በቁኝ ማለት ነው። በፊት እንዲህ ነበር
የማረገው
«አሁንስ?»
“አሁንም ላደርገው ተነሳሁ። ማርሰይ ወረድኩ። ግን ምንም
ሳላረግ ተመለስኩ።
«ወንዶችሽ እምቢ አሉሽ?»
በጉሮሮዋ ውስጥ ቅንዝረኛ ሳቋን እየሳቀች
“ትቀልዳለህ?» አለችኝ ተለውጬ ነው እንጂ። ወንድ መሄድ
ሱስ መሆኑ ቀረ»
«ሱስ መሆኑ ቀረ እንጂ መደረጉ ግን አልቀረም፣ እ?»
«መደረጉማ ለምን ይቀራል? የስሜት ደስታ አይደለም እንዴ?»
ይህን ጊዜ ቤቷ ልንደርስ አንድ መቶ ሜትር ያህል ቀርቶናል፡፡
ታሻሽው የነበረውን እጄን ለቀቀችና
ማን ይቅደም?» ብላ ትታኝ ሮጠች፡፡ እንዳልቀድማት ብዬ
ጫማዬን በሀይል እያስጮህኩ ተከተልኳት። እሷ እየጮኸች፣ እኔ
እየሳቅኩ ቤቷ ጋ ስንደርስ፣ በሩን ቀድማኝ በእጇ ነካችው
ቀደምኩህ!» አለችና በሩን ተደግፋ ቁና ቁና ስትተነፍስ፣
ጉንጮቿን በእጆቼ ይዤ ግምባሯን ሳምኳት እንደዚህ ለዋውጠኸኝ፣ በኋላ ያላንተ እንዳት ልሆን ነው?»
አለችኝ፡፡ በሀይል አሳዘነችኝ፡፡ ሆዴ ሽምቅቅ አለ፡፡ ወደኔ አስጠግቼ
ራሷን እየደባበስኩ ውይ የኔ ቆንጆ! እንድተውሽ አትፈልጊም እንዴ?» አልኳት
«አልፈልግም አልፈልግም አልፈልግም!» እያለች በጣም
ተጠጋችኝ፡ ራሷን አንገቴ ውስጥ ሸሸገች፡፡ እምባዋ አንገቴን ነካኝ
«እኔም ልተውሽ አልፈልግም፣ የኔ ቆንጆ፣ አልተውሽም፡፡
እስከመቼም አልተውሽም፡፡ ምንም ቢመጣ አልተውሽም» አልኳት
«እፈራለሁ፡፡ ካንት መለየቱን ሳስበው እፈራለሁ፡፡ አንተ አገርህ
ትሄድና፣ ከዚያ በኋላ አንገናኝም። እስከመቸም አላይህም፡፡ በቃ
ለዘለአለም?! ውይ! እቀፈኝ! እቀፈኝ!. . . መኖር እንዴት አስቸጋሪ
ነው!»
«አይዞሽ አንለያይም፣ የኔ ሲልቪ»
«አንለያይም?»
«አንለያይም። አይዞሽ አታስቢ። አሁን እንግባ»
አልጋ ውስጥ ላዬ ላይ አደረግኳትና፣ ጀርባዋንና አንገቷን
ጭንቅላቷን እየደባበስኩ ብዙ ጊዜ ከቆየን በኋላ፤
«አሁን ተለያይተን በወድያኛው ህይወት የምንገናኝ እንኳ
ቢሆን፣ ምናልባት እችለው ነበር» አለችኝ ግን መለያየቱ ለዘለአለም
ቢሆን፡ አንድ ጊዜ አይህና ከዚያ በኋላ ለዘለአለም ለዘለአለም
እስከመቸም የማንተያይ ስንሆን፣ በጣም ያስፈራኛል!» ብላ ተጠመጠመችብኝ
«አይዞሽ እንለያይም»
«አንለያይም?»
በሩ ተንኳኳ። ድንግጥ አለች
«አይዞሽ አይዞሽ»
በሩ እንደገና ተንኳኳ
«ማነው በይ» አልኳት
«ማነው?» አለች ጮክ ብላ
«ባህራም!»
ድንጋጤዋ ወደ ብሽቀት ተለወጠ። እየተነጫነጨች ተነስታ የሌሊት ካፖርቷን ራቁት ገላዋ ላይ ጣል አርጋመቀነቱን እየታጠ
ቀች ሄዳ በሩን ከፈተች
ባህራም «ይቅርታ በዚህ ሰአት ስላስቸገርኩ» እያለ ገባ። ጥቁር
ሙሉ ሱፍ ልብስ፣ ውሀ ሰማያዊ ሸሚዝ፣ ደማቅ ሰማያዊ ክራቫት::
ፂሙን ተላጭቶ፣ ፀጉሩን ወደ ኋላ አበጥሯል፡፡ ከጎንና ከጎን የበቀለው
ሽበት' የእርጅና ምልክት መሆኑ ቀርቶ ልዩ ጌጥ መስሏል፡፡ የድል
አድራጊነት ፈገግታ የሚጨፍርበት ፊቱ ወጣትነት ተላብሷል መጥቶ የተጋደምኩበት አልጋ አጠገብ ወምበር ላይ ሲቀመጥ
«እንዲህ ዘንጠህ የት ልትሄድ ነው? » አልኩት
ሲልቪ መጥታ ከጎኔ አልጋው ውስጥ ገባች
«እገሬ መግባቴ ነው» ከለ
“ልሰናበታችሁ ነው የመጣሁት»
«መሄድህ ነው በቃ?» አለችው ሲልቪ
“አዎን"
«ቆይ ዊስኪ ላምጣልህ» ብላ፣ ከአልጋው ወጥታ ወደ ወጥ ቤት
ሄደች፡፡ ቶሎ ከኪሱ አንድ ወረቀት አውጥቶ፣ ወምበር ላይ
የተሰቀለው ኮቴ ኪስ ውስጥ ከተተና፣ በሹክሹክታ
«ለብቻህ አንብበህ ቅደደው » አለኝ
"ላንተም ላምጣልህ? » አለች ከወጥ ቤቱ
«ለኔም ላንቺም አምጪ» አልኳት
ይዛ መጣች። ከልጋ ውስጥ ገባች። ዊስኪውን አነሳሁና ባሀራምን
«መልካም ጉዞ!» አልኩት
ፉት አልን
«ከመሄዴ በፊት ጥቂት ልነግርህ የሚገባኝ ነገር አለ» አለኝ።
ሲልቪ ትታን ልትሄድ ስትል «ካንቺ የሚደበቅ ያለበት አይደለም»
አላት
«እሺ» አልኩት
ብዙ ልነግርሀ በፈቀድኩ። ግን አብዛኛው የኢራን ኮሙኒስት
ፓርቲ ምስጢር ነው፡፡ አንተን አምንሀለሁ፡፡ ግን ፓርቲው
እንድነግርህ አይፈቅድልኝም»
«ይገባኛል፡፡ ምንም መናገር የለብህም»
«አውቃለሁ፡፡ ሁለት ነገር ብቻ በጠቅላላ ባጭሩ ልንገርህን
«ሁለት አመት ሙሉ በይሩት ነበርኩ፡፡ ግን ዩኒቨርሲቲው
ውስጥ የህክምና ትምህርት አልተማርኩም፡፡ ሌላ ስራ ነበረኝ። በቅርብ ምስራቅ ውስጥ ያሉትን የኢራን ኮሙኒስቶች ሳደራጅ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደሞ ከሻህ ሰላዮችና ከሲ.አይ.ኤ ጋር ረዥም ጦርነት ስናካሂድ ነበር። ሲ.አይ.ኤ ሊገድለኝ ሲሆን ጊዜ፣ ቱዴህ (የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ) እንድሸሽ አዘዘኝ። ወደ ኤክስ መጣሁ። እውነተኛ ስሜን
ልነግርህ አልችልም፡ ግን ባህራም አይደለም። ባሀራም ከፍሻር
በይሩት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ህክምና ይማር ነበር። በሱ ስም የውሽት ፓስፖርት አውጥቼ ነው፡፡
«ቤቶችህ ይህን ያውቃሉ?»
«ታላቅ ወንድሜ ያውቃል። ስም በቀየርኩ ቁጥር አዲስ ስሜን
በደብዳቤ ነግረዋለሁ፣ ከቤት ገንዘብ ሲመጣልኝ እሱ በአዲሱ ስሜ እየላከው ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድ ነገር አለኝ የምነግርህ»
ምን?»
«ደጋግመህ መልክህ የኢራንን ሻህ ይመስላል ብለኸኛል።
እውነትክን ነው:: ሻህ የስጋ ዘመዴ ነው»
አጭር ዝምታ
«ላሳየኸኝ ጓደኝነትና ለዋልክልኝ ውለታ ላመሰግንህ አልችልም፡፡
ስለዚህ ሳላመሰግንህ መሄዴ ነው» አለኝና ተነሳ፡፡ በቁሙ ዊስኪውን ጨልጦ፣ ብርጭቆውን ኮሞዲኖ ላይ አኖረው:: ልሸኘው ካልጋ ልነሳ ስል
«አትነሳ። ማኑ እዚህ ውጭ ይጠብቀኛል። አብረኸኝ ብትመጣ
ያለቅስብኛል፡፡ እሱ ሁልጊዜ እንደተጠነቀቀ ነው። ወዴት በኩል
እንደምንሄድ አንተ'ንኳ እንድታውቅ አይፈልግም» ይስቃል፡፡ ማኑን
ስለሚወደው ይስቅበታል። ከማኑ ጋር ለመሆን በመቻሉ እጅግ ደስ
ብሉታል፡፡ ወጣትነቱን እንደገና አግኝቷል። እጄን ዘረጋሁ:: ጨበጠኝ። በኔ በኩል ተንጠራርቶ ሲልቪን ሳማት። ሊሄድ ወደ በሩ በኩል ከዞረ በኋላ
«ለመሆኑ አልኩት ዞረ። ፊቱ ላይ ፈገግታ የለም፡፡ የኢራንን ሻሀ ይመስላል።አፍንጫው ትልቅ ነው
«ለመጀመሪያ ጊዜ
ሳገኝህ ሶስት አሜሪካኖች
ይዘውህ ሊደበድቡህ መጀመራቸው ነበር» አልኩት
“A bas les Yankecs!” አለኝ እየሳቀ
“A bas!" አልኩት
ሰአቱን አየ፡፡ ቸኩሏል
“ሊደበድቡህ ይዘውህ ሳለ፣ ማኑ ያስተማረሀን የመከላከል ዘዴ
ለምን አልተጠቀምክበትምን» አልኩት
«ተማሪዎች ይሁኑ ወይ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ይሁኑ እርግጠኛ አልነበርኩም። ምናልባት እኔን ፍለጋ የመጡ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ቢሆኑስ? ያን አይነት ያምባጓሮ ዘዴ ማወቄን ካወቁ ባህራም አለመሆኔን ይጠረጥራሉ። ለዚህ ነው:: በሎ ደህና ሁኑ። ማኑ ይጠብቀኛል»
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
....ከዚህ በፊት መፅሀፌ " እምቢ
ሲለኝ፣ አንተን አባርሬ ምን ነበር የማረገው መሰለህ?»
«ከመፅሀፍሽ ጋር የምትታገዪ ነበር የሚመስለኝ»
ተሳስተሀል። በየቀኑ ከምሳ በኋላ ማርሰይ እወርድና፡ ከሰአት
በኋላውን፣ ማታውን፣ አንድ አራት አምስት ወንድ ተኝቶኝ፣ ወደ
እኩለ ሌሊት ላይ ድክም ብሎኝ ወደ ኤክስ እመለሳለሁ:: በቀን
በቀኑ ይህን አረጋለሁ። አንድ ቀን ልሄድ ስዘጋጅ ፃፊ ፃፊ ይለኛል፡፡
መፃፍ እጀምራለሁ፡፡ ወንዶቹ በቁኝ ማለት ነው። በፊት እንዲህ ነበር
የማረገው
«አሁንስ?»
“አሁንም ላደርገው ተነሳሁ። ማርሰይ ወረድኩ። ግን ምንም
ሳላረግ ተመለስኩ።
«ወንዶችሽ እምቢ አሉሽ?»
በጉሮሮዋ ውስጥ ቅንዝረኛ ሳቋን እየሳቀች
“ትቀልዳለህ?» አለችኝ ተለውጬ ነው እንጂ። ወንድ መሄድ
ሱስ መሆኑ ቀረ»
«ሱስ መሆኑ ቀረ እንጂ መደረጉ ግን አልቀረም፣ እ?»
«መደረጉማ ለምን ይቀራል? የስሜት ደስታ አይደለም እንዴ?»
ይህን ጊዜ ቤቷ ልንደርስ አንድ መቶ ሜትር ያህል ቀርቶናል፡፡
ታሻሽው የነበረውን እጄን ለቀቀችና
ማን ይቅደም?» ብላ ትታኝ ሮጠች፡፡ እንዳልቀድማት ብዬ
ጫማዬን በሀይል እያስጮህኩ ተከተልኳት። እሷ እየጮኸች፣ እኔ
እየሳቅኩ ቤቷ ጋ ስንደርስ፣ በሩን ቀድማኝ በእጇ ነካችው
ቀደምኩህ!» አለችና በሩን ተደግፋ ቁና ቁና ስትተነፍስ፣
ጉንጮቿን በእጆቼ ይዤ ግምባሯን ሳምኳት እንደዚህ ለዋውጠኸኝ፣ በኋላ ያላንተ እንዳት ልሆን ነው?»
አለችኝ፡፡ በሀይል አሳዘነችኝ፡፡ ሆዴ ሽምቅቅ አለ፡፡ ወደኔ አስጠግቼ
ራሷን እየደባበስኩ ውይ የኔ ቆንጆ! እንድተውሽ አትፈልጊም እንዴ?» አልኳት
«አልፈልግም አልፈልግም አልፈልግም!» እያለች በጣም
ተጠጋችኝ፡ ራሷን አንገቴ ውስጥ ሸሸገች፡፡ እምባዋ አንገቴን ነካኝ
«እኔም ልተውሽ አልፈልግም፣ የኔ ቆንጆ፣ አልተውሽም፡፡
እስከመቼም አልተውሽም፡፡ ምንም ቢመጣ አልተውሽም» አልኳት
«እፈራለሁ፡፡ ካንት መለየቱን ሳስበው እፈራለሁ፡፡ አንተ አገርህ
ትሄድና፣ ከዚያ በኋላ አንገናኝም። እስከመቸም አላይህም፡፡ በቃ
ለዘለአለም?! ውይ! እቀፈኝ! እቀፈኝ!. . . መኖር እንዴት አስቸጋሪ
ነው!»
«አይዞሽ አንለያይም፣ የኔ ሲልቪ»
«አንለያይም?»
«አንለያይም። አይዞሽ አታስቢ። አሁን እንግባ»
አልጋ ውስጥ ላዬ ላይ አደረግኳትና፣ ጀርባዋንና አንገቷን
ጭንቅላቷን እየደባበስኩ ብዙ ጊዜ ከቆየን በኋላ፤
«አሁን ተለያይተን በወድያኛው ህይወት የምንገናኝ እንኳ
ቢሆን፣ ምናልባት እችለው ነበር» አለችኝ ግን መለያየቱ ለዘለአለም
ቢሆን፡ አንድ ጊዜ አይህና ከዚያ በኋላ ለዘለአለም ለዘለአለም
እስከመቸም የማንተያይ ስንሆን፣ በጣም ያስፈራኛል!» ብላ ተጠመጠመችብኝ
«አይዞሽ እንለያይም»
«አንለያይም?»
በሩ ተንኳኳ። ድንግጥ አለች
«አይዞሽ አይዞሽ»
በሩ እንደገና ተንኳኳ
«ማነው በይ» አልኳት
«ማነው?» አለች ጮክ ብላ
«ባህራም!»
ድንጋጤዋ ወደ ብሽቀት ተለወጠ። እየተነጫነጨች ተነስታ የሌሊት ካፖርቷን ራቁት ገላዋ ላይ ጣል አርጋመቀነቱን እየታጠ
ቀች ሄዳ በሩን ከፈተች
ባህራም «ይቅርታ በዚህ ሰአት ስላስቸገርኩ» እያለ ገባ። ጥቁር
ሙሉ ሱፍ ልብስ፣ ውሀ ሰማያዊ ሸሚዝ፣ ደማቅ ሰማያዊ ክራቫት::
ፂሙን ተላጭቶ፣ ፀጉሩን ወደ ኋላ አበጥሯል፡፡ ከጎንና ከጎን የበቀለው
ሽበት' የእርጅና ምልክት መሆኑ ቀርቶ ልዩ ጌጥ መስሏል፡፡ የድል
አድራጊነት ፈገግታ የሚጨፍርበት ፊቱ ወጣትነት ተላብሷል መጥቶ የተጋደምኩበት አልጋ አጠገብ ወምበር ላይ ሲቀመጥ
«እንዲህ ዘንጠህ የት ልትሄድ ነው? » አልኩት
ሲልቪ መጥታ ከጎኔ አልጋው ውስጥ ገባች
«እገሬ መግባቴ ነው» ከለ
“ልሰናበታችሁ ነው የመጣሁት»
«መሄድህ ነው በቃ?» አለችው ሲልቪ
“አዎን"
«ቆይ ዊስኪ ላምጣልህ» ብላ፣ ከአልጋው ወጥታ ወደ ወጥ ቤት
ሄደች፡፡ ቶሎ ከኪሱ አንድ ወረቀት አውጥቶ፣ ወምበር ላይ
የተሰቀለው ኮቴ ኪስ ውስጥ ከተተና፣ በሹክሹክታ
«ለብቻህ አንብበህ ቅደደው » አለኝ
"ላንተም ላምጣልህ? » አለች ከወጥ ቤቱ
«ለኔም ላንቺም አምጪ» አልኳት
ይዛ መጣች። ከልጋ ውስጥ ገባች። ዊስኪውን አነሳሁና ባሀራምን
«መልካም ጉዞ!» አልኩት
ፉት አልን
«ከመሄዴ በፊት ጥቂት ልነግርህ የሚገባኝ ነገር አለ» አለኝ።
ሲልቪ ትታን ልትሄድ ስትል «ካንቺ የሚደበቅ ያለበት አይደለም»
አላት
«እሺ» አልኩት
ብዙ ልነግርሀ በፈቀድኩ። ግን አብዛኛው የኢራን ኮሙኒስት
ፓርቲ ምስጢር ነው፡፡ አንተን አምንሀለሁ፡፡ ግን ፓርቲው
እንድነግርህ አይፈቅድልኝም»
«ይገባኛል፡፡ ምንም መናገር የለብህም»
«አውቃለሁ፡፡ ሁለት ነገር ብቻ በጠቅላላ ባጭሩ ልንገርህን
«ሁለት አመት ሙሉ በይሩት ነበርኩ፡፡ ግን ዩኒቨርሲቲው
ውስጥ የህክምና ትምህርት አልተማርኩም፡፡ ሌላ ስራ ነበረኝ። በቅርብ ምስራቅ ውስጥ ያሉትን የኢራን ኮሙኒስቶች ሳደራጅ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደሞ ከሻህ ሰላዮችና ከሲ.አይ.ኤ ጋር ረዥም ጦርነት ስናካሂድ ነበር። ሲ.አይ.ኤ ሊገድለኝ ሲሆን ጊዜ፣ ቱዴህ (የኢራን ኮሙኒስት ፓርቲ) እንድሸሽ አዘዘኝ። ወደ ኤክስ መጣሁ። እውነተኛ ስሜን
ልነግርህ አልችልም፡ ግን ባህራም አይደለም። ባሀራም ከፍሻር
በይሩት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ህክምና ይማር ነበር። በሱ ስም የውሽት ፓስፖርት አውጥቼ ነው፡፡
«ቤቶችህ ይህን ያውቃሉ?»
«ታላቅ ወንድሜ ያውቃል። ስም በቀየርኩ ቁጥር አዲስ ስሜን
በደብዳቤ ነግረዋለሁ፣ ከቤት ገንዘብ ሲመጣልኝ እሱ በአዲሱ ስሜ እየላከው ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድ ነገር አለኝ የምነግርህ»
ምን?»
«ደጋግመህ መልክህ የኢራንን ሻህ ይመስላል ብለኸኛል።
እውነትክን ነው:: ሻህ የስጋ ዘመዴ ነው»
አጭር ዝምታ
«ላሳየኸኝ ጓደኝነትና ለዋልክልኝ ውለታ ላመሰግንህ አልችልም፡፡
ስለዚህ ሳላመሰግንህ መሄዴ ነው» አለኝና ተነሳ፡፡ በቁሙ ዊስኪውን ጨልጦ፣ ብርጭቆውን ኮሞዲኖ ላይ አኖረው:: ልሸኘው ካልጋ ልነሳ ስል
«አትነሳ። ማኑ እዚህ ውጭ ይጠብቀኛል። አብረኸኝ ብትመጣ
ያለቅስብኛል፡፡ እሱ ሁልጊዜ እንደተጠነቀቀ ነው። ወዴት በኩል
እንደምንሄድ አንተ'ንኳ እንድታውቅ አይፈልግም» ይስቃል፡፡ ማኑን
ስለሚወደው ይስቅበታል። ከማኑ ጋር ለመሆን በመቻሉ እጅግ ደስ
ብሉታል፡፡ ወጣትነቱን እንደገና አግኝቷል። እጄን ዘረጋሁ:: ጨበጠኝ። በኔ በኩል ተንጠራርቶ ሲልቪን ሳማት። ሊሄድ ወደ በሩ በኩል ከዞረ በኋላ
«ለመሆኑ አልኩት ዞረ። ፊቱ ላይ ፈገግታ የለም፡፡ የኢራንን ሻሀ ይመስላል።አፍንጫው ትልቅ ነው
«ለመጀመሪያ ጊዜ
ሳገኝህ ሶስት አሜሪካኖች
ይዘውህ ሊደበድቡህ መጀመራቸው ነበር» አልኩት
“A bas les Yankecs!” አለኝ እየሳቀ
“A bas!" አልኩት
ሰአቱን አየ፡፡ ቸኩሏል
“ሊደበድቡህ ይዘውህ ሳለ፣ ማኑ ያስተማረሀን የመከላከል ዘዴ
ለምን አልተጠቀምክበትምን» አልኩት
«ተማሪዎች ይሁኑ ወይ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ይሁኑ እርግጠኛ አልነበርኩም። ምናልባት እኔን ፍለጋ የመጡ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች ቢሆኑስ? ያን አይነት ያምባጓሮ ዘዴ ማወቄን ካወቁ ባህራም አለመሆኔን ይጠረጥራሉ። ለዚህ ነው:: በሎ ደህና ሁኑ። ማኑ ይጠብቀኛል»
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...የማሪየስ አባት በየሁለትና ሃ'ስት ወር ፓሪስ ከተማ እየመጣ ልጁ
ከአያቱ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ያየዋል:: የገባውን ቃል አፍርሶ ስለሆነ የሚያየው ሰው እንዳያየው ተጠንቅቆ ከአሳቻ ሥፍራ በመደበቅ ነበር ልጁን የሚያየው።
ማሪየስ እንደማንኛውም ልጅ ትምህርት ቤት ገብቶ ይማራል። የታወቀ ጎበዝ አስተማሪ ከቤት ተቀጥርለት ትምህርቱን በሚገባ ይከታተላል: ኮሌጅ ከጨረሰ በኋላ የሕግ ትምህርት ለመከታተል ከሕግ ትምህርት ቤት ገባ፡፡
ለአያቱ ብዙም ፍቅር የለውም:: የአያቱ፡ አሽሙርና ንቀት ልቡን አቁስሎታል፡፡የወላጅ አባቱ ጉዳይ ግን ዘወትር ያሳስበዋል:: ልጁ በተፈጥሮው ጨዋ ረጋ ያለ ፤ በራሱ የሚተማመን ኩሩ ልጅ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ ፈሪሃ
እግዚአብሔር ያደረበት ነው፡፡ በ1827 ዓ.ም ማሪየስ የአሥራ ስምንት ዓመት ወጣት ነው:: አንድ ቀን ማታ አያቱ ከነበሩበት ክፍል ሲገባ ደብዳቤ በእጃቸው ይዘው ደረሰ፡፡
«ማሪየስ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ ነገ ጠዋት ወደ ቬርኖን ትሄዳለህ፡፡»
«ለምን?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
«አባትህን ለማየት::»
ማሪየስ ደነገጠ፡፡ አንድ ቀን ከአባቴ ጋር እገናኛለሁ የሚል ሀሳብ
በእውኑም ሆነ በሕልሙ አስቦት አያውቅም:: ምንም ነገር ከዚህ ይበልጥ አስደንጋጭና ያልተጠበቀ ሊሆንበት አይችልም ነበር፡፡
በሀገሪቱ ውስጥ ስለነበረው የፖለቲካ አቋም የተቃውሞ አሳብ
ሊኖረውም እያቱ እንደሚሉት አባቱ የቡርዥዋን አገዛዝ የሚቃወም
የማይረባ ወታደር» ነው:: በዚህ የተነሣ ለአባቱ የነበረው ፍቅር ይህን ያህል አልነበረም:: ከዚህም በላይ ወላጅ አባቱ እርሱን ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠቱ ጭካኔ ስለመሰለው ጠላው:: «አባቴ አይወደኝም» ሲል አምነ።
ይዞ በዚህ እንዳለ በዚያች ቅጽበት ያልጠበቀው ጥያቄ ከአያቱ ስለመጣዐበመደንገጡ የአዎንታም ሆነ የእምቢታ መልስ ለመስጠት አልቻልንም። አያቱ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡
«አባትህ ታሟል መሰለኝ፤ ሊያይህ ይፈልጋል::
በሚቀጥለው ቀን ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ማሪየስ ክሼርኖን ከተማ ደረሰ በመጀመሪያ ያገኘውን ሰው «የመሴይ ፓንት መርሲ ቤት የት እንደሆነ ያውቃሉ?ሲል ይጠይቃል::
ተጠያቂው ቤቱን ያውቅ ኖሮ አመላከተው:: ከቤቱ ሲደርስ በሩን
በመደብደብ አንኳኳ፡፡ አንዲት ሴት በሩን ከፈተችለት::
«መሴይ ፓንትመርሲ አሉ?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
ሴትዮዋ ደንግጣ መልስ ሳትሰጠው ዝም ብላ ቆመች::
«አሉ እንዴ?» ሲል እንደገና ጠየቀ፡፡
ለመኖሩ ግምባርዋን ወደ ላይ በመግፋት አረጋገጠችለት::
«ላነጋግራቸው እችላለሁ?»
እንደማይቻል ጭንቅላትዋን በመነቅነቅ ገለጸችለት::
«እኔኮ ልጃቸው ነኝ» አለ ማሪየስ፡፡ «እንደምመጣ ደግሞ ስለሚያወቁ
ይጠብቁኛል፡፡»
«ከእንግዲህ ወዲያ አይጠብቅህም» አለች ሴትዮዋ፡፡
በዚህ ጊዜ አተኩሮ ሲመለከታት ቀደም ሲል ታለቅስ እንደነበር አወቀ።
ወደ አንድ ክፍል ባመለከተችው ጊዜ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ክፍሉ
ውስጥ ሦስት ሰዎች ነበሩ፡፡ አንዱ ቆሞአል፤ ሌላው ተንበርክኮአል፡፡ ሦስተኛ ከመሬት ላይ ተንጋልሎ ተኝቷል፡፡ ተጋልሎ የተኛው አባቱ ነው::ከሁለቱ ሰዎች አንደኛው ሐኪም ሲሆን ሌላው ጸሉት የሚያደርሱ ቄስ ነበሩ፡፡
ኵሎኔሉ በጠና ከታመመ ሦስት ቀን ሆኖታል። ወዲያው ሕመሙ
እንደጀመረው ነበር ልጁ እንዲመጣለት በመልክተኛ ደብዳቤ ለመሴይ ጊልኖርማንድ የላከው:: ደብዳቤውን እንደላከ ሕመሙ እየጠናበት ሄደ።
ማሪየስ ቬርኖን በደረሰበት እለት ልጁ ከመድረሱ በፊት «ልጄ አልመጣም?
እሱ ካልመጣ እኔ ሄጄ እገናኘዋለሁ» እያለ ካልጋው ዘሎ ይወርዳል፡፡
ሠራተኞች ሊይዙት ቢሞክሩም ሊይዘት ባለመቻላቸው ከክፍሉ ወጥቶ ከበረዳ ሲደርስ ይወድቃል፡፡ እዚያው እንደወደቀ ሕይወቱ አለፈች፡፡
ሕይወቱ ከማለፉ በፊት ሐኪም እንዲመጣ ሰዎች ተራራጡ፡፡
ነገር ግን ሐኪሙ ከመድረሳቸው በፊት ኰሎኔሉ ሞተ:: ቄሱም ቢሆኑ ነፍሱ ከወጣ በኋላ እንጂ አስቀድመው አልደረሱም:: ልጁ ግን የደረሰው ዘግይቶ ነው::
ክፍሉ ውስጥ የነበረው መብራት ደብዛዛ ቢሆንም ከኩሎኔሉ ጉንጭ
ላይ ከመሞቱ በፊት እምባ መውረዱ ያስታውቃል፡፡ እንዲያውም እምባው
ጨርሶ አልደረቀም:፡ ያለቀሰው ልጁ በጊዜው ስላልደረሰለት ነበር፡፡
ማሪየስ ሰውዬውን አፍጥጦ ተመለከተው:: ለመጀመሪያና
ለመጨረሻ ጊዜ ነበር አባቱን ያየው:: የአባቱ ዓይኖች ሲገለጡም እርሱ ያያቸዋል እንጂ እነርሱ አያዩትም:: የአባቱ እጅ ተገልጦ ስለነበረ የጦር
ሜዳ ቁስሎቹ ጠባሳ በብዛት ይታያሉ፡፡ ከፊቱም ላይ ትልቅ ጠባሳ አለ፡፡
አባቱ እንደሆነና ሕይወቱ እንዳለፈች ማሪየስ አወቀ፡፡ በድንጋጤ ክው ስላለ
ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ያዘነው ሀዘን ወደር አልነበረውም፡፡ እንኳን
የወለደው አባቱ ማንም ሰው ቢሆን እንደዚያ ተዘርሮና ሞቶ ቢያይ በጣም ማዘኑ አይቀርም።
ሀዘን፤ መሪር ሀዘን ከዚያች ክፍል ውስጥ ሰፍኖአል፡፡ ሠራተኛዋ
ከጥግ ቆማ ታነባዋለች፡፡ ቄሱ ይጸልያሉ፤ ግን እየጸለዩ ሲንሰቀሰቁ ይሰማል፡፡
ሐኪሙ ወዲያው፧ ወዲያው ዓይናቸውን በመሐረብ ይጠርጋሉ፡፡ ሬሳውም
ቢሆን የሚያለቅስ ይመስላል::
ሐኪሙ፤ ቄሱ፤ ሴትዬዋ ቃል ሳይተነፍሱ ማሪየስን አዩት:: ከውጭ የመጣ እንግዳ እሱ ብቻ ነው:: ማሪየስ ከነበረበት ትንሽ ነቅነቅ አለ። በጣም እፍረት ተሰማው፡፡ ያደረገውን ቆብ አውልቆ በእጅ ይዞት ስለነበር
ሳይታወቀው ከእጁ አምልጦ ከመሬት ወደቀ፡፡ ነገር ግን በጣም ከማዘኑ የተነሣ ቆቡን እንኳን ለመያዝ አቅም እንደሌለው ለማሳየት እንጂ እውነትም
አምልጦት አልነበረም::
ስለአባቱ የነበረውን አመለካከትና ግምት አስታውሶ ተጸጸተ::
መጸጸት ብቻ ሳይሆን ራሱን በጣም ነቀፈ:: ግን ጥፋቱ የእርሱ ነው? ኰሎኔሉ ወደኋላ የተወው ሀብት አልነበረም:: ከቤቱ ውስጥ የነበሩት እቃዎች ተሽጠው ለቀብሩ የወጣውን ወጪ እንኳን ለመሸፈን አልቻሉም፡፡ሠራተኛዋ አንዲት ወረቀት አግኝታ ለማሪየስ ሰጠችው:: ኩሎኔሉ ከመሞቱ
በፊት የጻፈው ማስታወሻ ሲሆን ቃሉም የሚከተለው ነው፡፡
«ለምወድህ ልጄ ፤ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ፡፡ እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል
ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ከወረቀቱ ጀርባ ላይ ኲሉኔሉ የጻፈው ማስታወሻ ደግሞ ‹‹በዚሁ በዋተርሉ ጦርነት አንድ የሃምሣ አለቃ ሕይወቴን አድኖአል:: ስሙ ቴናድዬ ይባላል:: ከፓሪስ ከተማ ወጣ ብሎ
ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንዲት አነስተኛ ሆቴል እንደነበረው አውቃለሁ:: ድንገት ካገኘኸው በተቻለህ እርሱን እርዳልኝ» የሚል ነበር፡፡
የአባቱ ፍቅር አስገድዶት ሳይሆን «የሞተን አክብር.» ብሎ በሚገፋፋን ውስጣዊ ኃይል ተመስጦ ማሪየስ ወረቀቱን በኃይል ጨመደደው::
ስለኩሎኔሉ ከዚያ በኋላ የታወቀ ነገር የለም:: ዩኒፎርሙንና
ጉራዴውን መሴይ ጊልኖርማንድ ለውራጅ እቃ ሸማች ሸጡት፡፡ ኰሎኔሉ የተከላቸውን አበቦች ጎረቤቱ ቀጥፈውና አትክልቱን አበላሽተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ድራሹን አጠፉት::
ማሪየስ ለሁለት ቀን እዚያው ቬርኖን ቆይቶ ከቀብሩ ሥነሥርዓት
በኋላ ወደ ፓሪስ ተመለሰ፡፡ ከዚያም የአባቱ መሞት ብዙም ሳይረብሸው ትምህርቱን ቀጠለ፡፡ ኵሎኔሉ በሞተ በሁለተኛው ቀን ተቀበረ፤ በሦስተኛ ቀን ተረሳ፡፡
ማሪየስ ለጥቂት ቀናት ከኮቱ ኮሌታ ላይ ጥቁር ጨርቅ አደረገ፡፡
የሀዘን ምልክት መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ሌላ የተደረገ ነገር አልነበረም::
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
...የማሪየስ አባት በየሁለትና ሃ'ስት ወር ፓሪስ ከተማ እየመጣ ልጁ
ከአያቱ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ያየዋል:: የገባውን ቃል አፍርሶ ስለሆነ የሚያየው ሰው እንዳያየው ተጠንቅቆ ከአሳቻ ሥፍራ በመደበቅ ነበር ልጁን የሚያየው።
ማሪየስ እንደማንኛውም ልጅ ትምህርት ቤት ገብቶ ይማራል። የታወቀ ጎበዝ አስተማሪ ከቤት ተቀጥርለት ትምህርቱን በሚገባ ይከታተላል: ኮሌጅ ከጨረሰ በኋላ የሕግ ትምህርት ለመከታተል ከሕግ ትምህርት ቤት ገባ፡፡
ለአያቱ ብዙም ፍቅር የለውም:: የአያቱ፡ አሽሙርና ንቀት ልቡን አቁስሎታል፡፡የወላጅ አባቱ ጉዳይ ግን ዘወትር ያሳስበዋል:: ልጁ በተፈጥሮው ጨዋ ረጋ ያለ ፤ በራሱ የሚተማመን ኩሩ ልጅ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ ፈሪሃ
እግዚአብሔር ያደረበት ነው፡፡ በ1827 ዓ.ም ማሪየስ የአሥራ ስምንት ዓመት ወጣት ነው:: አንድ ቀን ማታ አያቱ ከነበሩበት ክፍል ሲገባ ደብዳቤ በእጃቸው ይዘው ደረሰ፡፡
«ማሪየስ» አሉ መሴይ ጊልኖርማንድ ነገ ጠዋት ወደ ቬርኖን ትሄዳለህ፡፡»
«ለምን?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
«አባትህን ለማየት::»
ማሪየስ ደነገጠ፡፡ አንድ ቀን ከአባቴ ጋር እገናኛለሁ የሚል ሀሳብ
በእውኑም ሆነ በሕልሙ አስቦት አያውቅም:: ምንም ነገር ከዚህ ይበልጥ አስደንጋጭና ያልተጠበቀ ሊሆንበት አይችልም ነበር፡፡
በሀገሪቱ ውስጥ ስለነበረው የፖለቲካ አቋም የተቃውሞ አሳብ
ሊኖረውም እያቱ እንደሚሉት አባቱ የቡርዥዋን አገዛዝ የሚቃወም
የማይረባ ወታደር» ነው:: በዚህ የተነሣ ለአባቱ የነበረው ፍቅር ይህን ያህል አልነበረም:: ከዚህም በላይ ወላጅ አባቱ እርሱን ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠቱ ጭካኔ ስለመሰለው ጠላው:: «አባቴ አይወደኝም» ሲል አምነ።
ይዞ በዚህ እንዳለ በዚያች ቅጽበት ያልጠበቀው ጥያቄ ከአያቱ ስለመጣዐበመደንገጡ የአዎንታም ሆነ የእምቢታ መልስ ለመስጠት አልቻልንም። አያቱ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡
«አባትህ ታሟል መሰለኝ፤ ሊያይህ ይፈልጋል::
በሚቀጥለው ቀን ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ማሪየስ ክሼርኖን ከተማ ደረሰ በመጀመሪያ ያገኘውን ሰው «የመሴይ ፓንት መርሲ ቤት የት እንደሆነ ያውቃሉ?ሲል ይጠይቃል::
ተጠያቂው ቤቱን ያውቅ ኖሮ አመላከተው:: ከቤቱ ሲደርስ በሩን
በመደብደብ አንኳኳ፡፡ አንዲት ሴት በሩን ከፈተችለት::
«መሴይ ፓንትመርሲ አሉ?» ሲል ማሪየስ ጠየቀ::
ሴትዮዋ ደንግጣ መልስ ሳትሰጠው ዝም ብላ ቆመች::
«አሉ እንዴ?» ሲል እንደገና ጠየቀ፡፡
ለመኖሩ ግምባርዋን ወደ ላይ በመግፋት አረጋገጠችለት::
«ላነጋግራቸው እችላለሁ?»
እንደማይቻል ጭንቅላትዋን በመነቅነቅ ገለጸችለት::
«እኔኮ ልጃቸው ነኝ» አለ ማሪየስ፡፡ «እንደምመጣ ደግሞ ስለሚያወቁ
ይጠብቁኛል፡፡»
«ከእንግዲህ ወዲያ አይጠብቅህም» አለች ሴትዮዋ፡፡
በዚህ ጊዜ አተኩሮ ሲመለከታት ቀደም ሲል ታለቅስ እንደነበር አወቀ።
ወደ አንድ ክፍል ባመለከተችው ጊዜ ወደ ክፍሉ ገባ፡፡ ክፍሉ
ውስጥ ሦስት ሰዎች ነበሩ፡፡ አንዱ ቆሞአል፤ ሌላው ተንበርክኮአል፡፡ ሦስተኛ ከመሬት ላይ ተንጋልሎ ተኝቷል፡፡ ተጋልሎ የተኛው አባቱ ነው::ከሁለቱ ሰዎች አንደኛው ሐኪም ሲሆን ሌላው ጸሉት የሚያደርሱ ቄስ ነበሩ፡፡
ኵሎኔሉ በጠና ከታመመ ሦስት ቀን ሆኖታል። ወዲያው ሕመሙ
እንደጀመረው ነበር ልጁ እንዲመጣለት በመልክተኛ ደብዳቤ ለመሴይ ጊልኖርማንድ የላከው:: ደብዳቤውን እንደላከ ሕመሙ እየጠናበት ሄደ።
ማሪየስ ቬርኖን በደረሰበት እለት ልጁ ከመድረሱ በፊት «ልጄ አልመጣም?
እሱ ካልመጣ እኔ ሄጄ እገናኘዋለሁ» እያለ ካልጋው ዘሎ ይወርዳል፡፡
ሠራተኞች ሊይዙት ቢሞክሩም ሊይዘት ባለመቻላቸው ከክፍሉ ወጥቶ ከበረዳ ሲደርስ ይወድቃል፡፡ እዚያው እንደወደቀ ሕይወቱ አለፈች፡፡
ሕይወቱ ከማለፉ በፊት ሐኪም እንዲመጣ ሰዎች ተራራጡ፡፡
ነገር ግን ሐኪሙ ከመድረሳቸው በፊት ኰሎኔሉ ሞተ:: ቄሱም ቢሆኑ ነፍሱ ከወጣ በኋላ እንጂ አስቀድመው አልደረሱም:: ልጁ ግን የደረሰው ዘግይቶ ነው::
ክፍሉ ውስጥ የነበረው መብራት ደብዛዛ ቢሆንም ከኩሎኔሉ ጉንጭ
ላይ ከመሞቱ በፊት እምባ መውረዱ ያስታውቃል፡፡ እንዲያውም እምባው
ጨርሶ አልደረቀም:፡ ያለቀሰው ልጁ በጊዜው ስላልደረሰለት ነበር፡፡
ማሪየስ ሰውዬውን አፍጥጦ ተመለከተው:: ለመጀመሪያና
ለመጨረሻ ጊዜ ነበር አባቱን ያየው:: የአባቱ ዓይኖች ሲገለጡም እርሱ ያያቸዋል እንጂ እነርሱ አያዩትም:: የአባቱ እጅ ተገልጦ ስለነበረ የጦር
ሜዳ ቁስሎቹ ጠባሳ በብዛት ይታያሉ፡፡ ከፊቱም ላይ ትልቅ ጠባሳ አለ፡፡
አባቱ እንደሆነና ሕይወቱ እንዳለፈች ማሪየስ አወቀ፡፡ በድንጋጤ ክው ስላለ
ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ያዘነው ሀዘን ወደር አልነበረውም፡፡ እንኳን
የወለደው አባቱ ማንም ሰው ቢሆን እንደዚያ ተዘርሮና ሞቶ ቢያይ በጣም ማዘኑ አይቀርም።
ሀዘን፤ መሪር ሀዘን ከዚያች ክፍል ውስጥ ሰፍኖአል፡፡ ሠራተኛዋ
ከጥግ ቆማ ታነባዋለች፡፡ ቄሱ ይጸልያሉ፤ ግን እየጸለዩ ሲንሰቀሰቁ ይሰማል፡፡
ሐኪሙ ወዲያው፧ ወዲያው ዓይናቸውን በመሐረብ ይጠርጋሉ፡፡ ሬሳውም
ቢሆን የሚያለቅስ ይመስላል::
ሐኪሙ፤ ቄሱ፤ ሴትዬዋ ቃል ሳይተነፍሱ ማሪየስን አዩት:: ከውጭ የመጣ እንግዳ እሱ ብቻ ነው:: ማሪየስ ከነበረበት ትንሽ ነቅነቅ አለ። በጣም እፍረት ተሰማው፡፡ ያደረገውን ቆብ አውልቆ በእጅ ይዞት ስለነበር
ሳይታወቀው ከእጁ አምልጦ ከመሬት ወደቀ፡፡ ነገር ግን በጣም ከማዘኑ የተነሣ ቆቡን እንኳን ለመያዝ አቅም እንደሌለው ለማሳየት እንጂ እውነትም
አምልጦት አልነበረም::
ስለአባቱ የነበረውን አመለካከትና ግምት አስታውሶ ተጸጸተ::
መጸጸት ብቻ ሳይሆን ራሱን በጣም ነቀፈ:: ግን ጥፋቱ የእርሱ ነው? ኰሎኔሉ ወደኋላ የተወው ሀብት አልነበረም:: ከቤቱ ውስጥ የነበሩት እቃዎች ተሽጠው ለቀብሩ የወጣውን ወጪ እንኳን ለመሸፈን አልቻሉም፡፡ሠራተኛዋ አንዲት ወረቀት አግኝታ ለማሪየስ ሰጠችው:: ኩሎኔሉ ከመሞቱ
በፊት የጻፈው ማስታወሻ ሲሆን ቃሉም የሚከተለው ነው፡፡
«ለምወድህ ልጄ ፤ ዋተርሉ ጦር ሜዳ ላይ በተደረገው ጦርነት
ስለፈጸምኩት ጀብዱ የባሮንነት ማዕረግ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ማዕረጉን በደሜ የዋጀሁት ስለሆነ ለልጄ ማውረስ እችላለሁ፡፡ እኔ አሁን ማዕረጉ ይገባዋል
ወይም አይገባውም ብዬ መናገር የለብኝም:: ከወረቀቱ ጀርባ ላይ ኲሉኔሉ የጻፈው ማስታወሻ ደግሞ ‹‹በዚሁ በዋተርሉ ጦርነት አንድ የሃምሣ አለቃ ሕይወቴን አድኖአል:: ስሙ ቴናድዬ ይባላል:: ከፓሪስ ከተማ ወጣ ብሎ
ሞንትፌርሜ ከተባለ ሥፍራ አንዲት አነስተኛ ሆቴል እንደነበረው አውቃለሁ:: ድንገት ካገኘኸው በተቻለህ እርሱን እርዳልኝ» የሚል ነበር፡፡
የአባቱ ፍቅር አስገድዶት ሳይሆን «የሞተን አክብር.» ብሎ በሚገፋፋን ውስጣዊ ኃይል ተመስጦ ማሪየስ ወረቀቱን በኃይል ጨመደደው::
ስለኩሎኔሉ ከዚያ በኋላ የታወቀ ነገር የለም:: ዩኒፎርሙንና
ጉራዴውን መሴይ ጊልኖርማንድ ለውራጅ እቃ ሸማች ሸጡት፡፡ ኰሎኔሉ የተከላቸውን አበቦች ጎረቤቱ ቀጥፈውና አትክልቱን አበላሽተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ድራሹን አጠፉት::
ማሪየስ ለሁለት ቀን እዚያው ቬርኖን ቆይቶ ከቀብሩ ሥነሥርዓት
በኋላ ወደ ፓሪስ ተመለሰ፡፡ ከዚያም የአባቱ መሞት ብዙም ሳይረብሸው ትምህርቱን ቀጠለ፡፡ ኵሎኔሉ በሞተ በሁለተኛው ቀን ተቀበረ፤ በሦስተኛ ቀን ተረሳ፡፡
ማሪየስ ለጥቂት ቀናት ከኮቱ ኮሌታ ላይ ጥቁር ጨርቅ አደረገ፡፡
የሀዘን ምልክት መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ሌላ የተደረገ ነገር አልነበረም::
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ለአንዳፍታም ቢሆን እንኳን ቱናትን መለየት ያሸብራል፡ መቼስ እንዲህ የሚያደርገኝ ልጅነቷ ወይም መላመዳችን ወይ ደግሞ ገዳሜ ስለሆነች ብቻ አይመስለኝም፡ ታዲያ ምንድነዉ?
ብቻ ክብድ ብሎኛል፡
ደረስሁ።
ከጨዋታ ይልቅ ለዝምታ የሚያመቸዉን በትላልቅ ሀገር በቀል ዛፎች የተሞላዉን ግቢ፣ በተለያየ ዕድሜ የሚገኙት ሕጻናት ይቦርቁበታል። አንዳንዶች ክብ ሠርተዉ፣ አንዳንዶች በመስመር ሆነዉ፣ ሌሎች ዝብርቅርቅ ብለዉ የልባቸዉን ይጫወቱበታል፡ አለፍ ብሎ ባለዉ ሜዳ ላይ ሰፊ ምንጣፍ ተነጥፎላቸዉ ጨቅላዎች ይንከባለላሉ ከእነሱ በወራት
ዕድሜ ከፍ ያሉት ደግሞ ራሳቸዉን ችለዉ ለመቆም ይዉተረተራሉ
የሕጻናቱ ተንከባካቢዎች እንደየምድባቸዉ የሚቆሙት ቆመዉ፣ ያቀፉት ደግሞ ተቀምጠዉ በየትዕይንቱ ይደሰታሉ።
መሥራትስ እንደ እነሱ ነዉ› አልሁኝ፣ በቅናት።
ሆኖም ሥጋቴ ሊያልፍልኝ አልቻለም: እንዲሁ ከመኪናዬ ወረድሁና ቱናትን ከአልጋዋ አንስቼ አቀፍኋትና፣ የግቢዉ አማካይ የሚሆን ሥፍራ ላይ ቆምሁ፡፡ በየትኛዉ ቢሮ የትኛዉን ሰዉ ማናገር እንዳለብኝ በዓይኖቼ
ወዲያ ወዲህ ስል አንዲት በልተት ያሉ ሴትዮ ቀረቡኝ፡
“እንኳን በደህና መጣችሁ” አሉ፣ ልብ በሚሞላ ፈገግታ እኔንም
ቱናትንም አይተዉ ይበልጥ እየቀረቡን፡፡
“እንኳን ደህና አገኘኋችሁ” አልሁ፣ አንገቴን ወደ ጉልበታቸዉ
በመስበር ለትሕትናቸዉ ጭምር አክብሮት እየሰጠሁት፡
እዉነትም እነ እመዋ ነገሮችን ጨራርሰዉልኝ ኖሮ፣ ማነሽ የሚለኝ ሰዉ ቀርቶ ቅጽ እንድሞላ እንኳን የጠየቀኝ ሰዉ የለም፡ ቀድሜ ያገኘኋቸዉ ሴትዮ ለቱናት የተመደበላትን ማደሪያ ክፍል፣ ክፍሉን የሚጋሯትን
ሕጻናት፣ ያለማስታጎል እንዲከታተላት የተመደበላትን ነርስ፣ የምግቦቿን ዝርዝር መርሐ ግብር፣ልብሶቿን እና ሌሎች ነገሮችን በዚያዉ በማይለዋወጥ ትሕትናቸዉ ከገለጹልኝ በኋላ፣ ሥጋት ወይም አስታያየት
ይኖረኝ እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡
“እንግዲያዉ መዋእለ ሕጻናት ብቻ አይደለማ ይኼማ?” አልኋቸዉ:
“ትክክል። ያዉ እንደምታዉቂዉ” አሉ፣ ደጋገሜ አንቺ እንዲሉኝ
የለመንኋቸዉን እንደ ምንም ተስማምተዉልኝ፡ “ያዉ እንደምታዉቂዉ አብዛኛዉ የማኅበራች አገልጋዮች ሌት ከቀ ሥራ ላይ ናቸዉ። በዚህም
የተነሳ ለልጆቻቸዉ በቂ እክብካቤ ለማድረግ ይቸገራሉ። ይኼ የሕጻናት መዋያ ከተከፈተ ወዲህ ግን እንደየአገልግሎት ጸባያቸዉ፣ ሙሉ ኃላፊነቱን ለእኛ ለመተዉ የተፈቀደላቸዉ አገልጋዮች አሉ: ሥራቸዉ ፋታ የሚሰጣቸዉ ያሉ እንደሆነ ግን ኃላፊነት የም ወስድላቸዉ ወይ ቀኑን ወይ ማታዉን ብቻ ይሆናል ማለት ነዉ” አሉኝ፣ ቱናትን ባዘጋጁላት
አልጋዋ ላይ እያሳረፏት፡
“ታዲያ” አልሁኝ፣ ከሁሉም ቅድሚያ ለቱናት የሚበላ እንዲሰጡልኝ ለመጠየቅ እንደገና እየዳዳሁ የአንገት ሰላምታ በርቀት ሰጥተዉኝ ከነበሩት ሴቶች አንደኛዋ፣ የልቤን አዉቃልኝ ይሁን የቱናትን ቡዝዝ ማለት አይታ እንደሆነ እንጃ፣ ትኩስ የሥጋ ፍትፍት አመጣችላት። ደቀቅ
ያለዉን የሥጋ አመታሮ በቀይ እንጀራ ፈትፍታ አምጥታ ስታጎርሳት እኔ ምራቄን ብዉጥም፣ቱናት ግን እምቢ አለች: ለማጫወት ብትሞክራት ሁሉ ለማልቀስ ተነፋነፈች።
“ግድ የለም” አሉ፣ ባልቴቷ። “ግድየለም፤ እንግድነት ተሰምቷት ነዉ። ትንሽ ትፋሽ ትዉሰድና እኔ አጫዉቼ አበላታለሁ”
“አይ አልሁኝ፣ ሥጋቴን መደበቅ እያቃተኝ፡
“ግድ የለሽም”
“እንዲያዉ ዛሬ እምብዛም ሳትበላ ነዉ የዋለችዉ”
“ሐሳብ አይግባሽ፤ አጫዉቼ አበላታለሁ”
“እንግዲህ ምን እላለሁ፣ እግዚአብሔር ይስጥልኝ ከማለት በቀር አልኋቸዉ ኹለቱንም፣ ስለ በጎ አድራጎታቸዉ፡
"ተዪ ተዪ: እኛ ነን ማመስገን ያለብን: እንኳንም እግዚአብሔር ልዩ አድርጎ የሰጠሽ ልጅሽ እንድናገለግላት ዕድሉን ሰጠሸን”
“አይ… እንዲያዉ ወድጄ እንኳን አይደለም ያመጣኋት: ልጄ ከብዳኝ ወይ ደግሞ ከእሷ የሚበልጥብኝ ሥራ ኖሮብኝም አይደለም”
“ይገባኛል”
“የሆነዉ ሆኖ እንግዲህ ከኹለት ወይ ከሦስት ሰዓት በላይ
አላስቸግራችሁም”
“ማስቸገር? የለም የለም: ለእሷ ከምናደርግላት ይልቅ፣ እሷ ለእኛ
የምታደርግልን ይበልጥብናል። ከባሪዎቹ እኛዉ ነን''
“ይሁን” ብዬ፣ ወጣሁ።
ለቅሶዋን ከኋላዬ እየሰማሁ፣ እንደ ምንም ጨክኜ ወጣሁ ወደ ጦር ሜዳ እየኼድሁ እንደሆነ ነዉ የሚሰማኝ፡ ከወንድሞቼ እና
ከእህቶቼ፣ በተለይም ከጃሪም ጋር ፊት ለፊት እስከምገጥም ቸኩያለሁ።እሱም ቢሆን ሌላ ምንም ምርጫ አልተዉልኝም፡፡
‹ምን ይሉት ፍርጃ ነዉ ግን? ኧረ እንደ ዋዛ የት ነዉ የደረስነዉ
በማርያም? እያልሁ እንዲችዉ እንደ ተብሰለሰልሁ፣ በአዲስ አበባ
ዩኒቨርስቲ ዋናዉ ግቢ በኩል ባለዉ ቁልቁለት ወረድሁ።
ለነገሩ ለምን በእነሱ ብቻ እፈርዳለሁ? ጥፋቱ የራሴም ጭምር አይደል?እነሱ ሆኑብኝና ተለማመጥኋቸዉ፡ የእኔ በሕይወት መኖር በእነሱ ፈቃድ እስኪመስል ድረስ ግፊያቸዉን ሁሉ ቻልሁላቸዉ᎓ የጃሪም ወንድምነት
ቢቀርብኝ እሞት ይመስል፣ ያለ ጥፋቴ ጭምር ማረኝ ማረኝ አልሁት።
ቆይ፤ እዉነት ግን አልሞትም? ያለ ጃሪም ወንድምነት፣ ያለ እህቶቼ
እህትነት ምንድን ነኝ እኔ?
ወደ ማኅበራችን ሕንጻ የሚያደርሰኝን መንገድ እንደ ተያያዝሁት፣ የዛፍ እና የንብ ሽርክና በልቡናዬ ክችች አለብኝ፡፡
ሠራተኛዋ ንብ ለማኅበረ ንቧ የሚሆነዉን ምግብ ለመቅሰም አበባ ወዳለው ዛፍ ታርፋለች:: ከአበባዉ ላይ የምታገኘዉን ዕጩ ማር ከቀሰመች በኋላ ተጨማሪ ፍለጋ ወደ ሌላ ባለ አበባ ዛፍ ትሄዳለች: ነገር ግን ከዛፋ
በምትነሳበት ጊዜ፣ የአበባዉ ወንዴ ዘር በጸጉራም አካሏ ላይ ተሳፍሮ ይከተላታል። ወደ ቀጣዩ የአበባ ዛፍ በምታርፍ ጊዜም፣ ያ ከዚያኛዉ ዛፍ ያመጣችዉ ወንዴ ዘር፣ እዚህኛዉ ዘንድ ካለዉ የአበባዉ ሴቴ ዘር ጋር ይገናኛል፡ በዚህም ምክንያት፣ ንቧ ምግቧን ፍለጋ ከዛፍ ዛፍ ባረፈች
ቁጥር፣ የአበባ ዛፎች እንዲራቡ ታደርጋለች ማለት ነዉ ንብ ያለ አበባ ማለት እንግዲህ ያለ ምግብ፤ አበባም ያለ ንብ ማለት ደግሞ ያለ መራባት ስለሆነ ተከላክለዉ አያዉቁም:: እርስ በእርስ ቢከላከሉ፣ አንዳቸዉም መኖር እንደማይችሉ ኹለቱም ጠንቅቀዉ ያዉቁታል።
ስለዚህ ንብ እና አበባ አይለማመኑም:: አለመለማመን ብቻም ሳይሆን፣ ነፍሳቸዉ እስኪገባ ድረስ ይዋደዳሉ
እንደ እዉነቱ፣ እኔና ጃሪምም ሆንን ከሌሎች እህትና ወንድሞቻችንም
ጋር ግን፣ አበባና ንብ ብቻ አይደለንም፡፡ ወይ ንብ እና ንብ፣ ወይ አበባና አበባ ነን፡ ያዉም ወይ የአንድ እናት ንብ እናት አበቦች ነን፡፡ እንዲያዉ እሱም አጉል ሆኖ ቢፈርስ ግን፣ ቢያንስ ንቦች፣ ወይ ደግሞ የአንድ እንደ አበባና ንብ እንኳን መሆን እንዴት ያቅተናል?
የእኔም እጅ አለበት፡፡
አዎ፣ አለበት!
እኔ ያለ እነሱ መኖር እንደማልችል ብቻ እንጂ፣ እነሱም ያለ እኔ መኖር
እንደማይችሉ ነግሪያቸዉ አላዉቅም አበባ የንብን ጥቅም ባያዉቅ ኖሮ አያከብረዉም: የማያከብረዉን ደግሞ የሚወድ የለም፡ መናቅን እንጂ፣በእጄ ነሽ፣ ብለቅሽ ያልቅልሻል፣ ተሸከምሁሽ፣ በደልሽኝ ማለትን እንጂ
እንደ'ኔ ማለትን ያስተዋል፡፡ እህትነቴ እንዲተናነቃቸዉ፣ እነ ጃሪም እዚህ እንዲደርሱ የእኔም ሚና አለበት፡፡
“የት ናት?” አልሁት ባልቻን፣ ከራሴ ጋር እንዲህ እየተዋቀስሁ ወደ
ሲራክ ፯ ማዕከል ደርሼ ቢሮዉ ዉስጥ ያገኘሁት ከኹለት ሰዎች ጋር እየተነጋገረ ቢሆንም፣ ምንም ሳይመስለኝ፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...ለአንዳፍታም ቢሆን እንኳን ቱናትን መለየት ያሸብራል፡ መቼስ እንዲህ የሚያደርገኝ ልጅነቷ ወይም መላመዳችን ወይ ደግሞ ገዳሜ ስለሆነች ብቻ አይመስለኝም፡ ታዲያ ምንድነዉ?
ብቻ ክብድ ብሎኛል፡
ደረስሁ።
ከጨዋታ ይልቅ ለዝምታ የሚያመቸዉን በትላልቅ ሀገር በቀል ዛፎች የተሞላዉን ግቢ፣ በተለያየ ዕድሜ የሚገኙት ሕጻናት ይቦርቁበታል። አንዳንዶች ክብ ሠርተዉ፣ አንዳንዶች በመስመር ሆነዉ፣ ሌሎች ዝብርቅርቅ ብለዉ የልባቸዉን ይጫወቱበታል፡ አለፍ ብሎ ባለዉ ሜዳ ላይ ሰፊ ምንጣፍ ተነጥፎላቸዉ ጨቅላዎች ይንከባለላሉ ከእነሱ በወራት
ዕድሜ ከፍ ያሉት ደግሞ ራሳቸዉን ችለዉ ለመቆም ይዉተረተራሉ
የሕጻናቱ ተንከባካቢዎች እንደየምድባቸዉ የሚቆሙት ቆመዉ፣ ያቀፉት ደግሞ ተቀምጠዉ በየትዕይንቱ ይደሰታሉ።
መሥራትስ እንደ እነሱ ነዉ› አልሁኝ፣ በቅናት።
ሆኖም ሥጋቴ ሊያልፍልኝ አልቻለም: እንዲሁ ከመኪናዬ ወረድሁና ቱናትን ከአልጋዋ አንስቼ አቀፍኋትና፣ የግቢዉ አማካይ የሚሆን ሥፍራ ላይ ቆምሁ፡፡ በየትኛዉ ቢሮ የትኛዉን ሰዉ ማናገር እንዳለብኝ በዓይኖቼ
ወዲያ ወዲህ ስል አንዲት በልተት ያሉ ሴትዮ ቀረቡኝ፡
“እንኳን በደህና መጣችሁ” አሉ፣ ልብ በሚሞላ ፈገግታ እኔንም
ቱናትንም አይተዉ ይበልጥ እየቀረቡን፡፡
“እንኳን ደህና አገኘኋችሁ” አልሁ፣ አንገቴን ወደ ጉልበታቸዉ
በመስበር ለትሕትናቸዉ ጭምር አክብሮት እየሰጠሁት፡
እዉነትም እነ እመዋ ነገሮችን ጨራርሰዉልኝ ኖሮ፣ ማነሽ የሚለኝ ሰዉ ቀርቶ ቅጽ እንድሞላ እንኳን የጠየቀኝ ሰዉ የለም፡ ቀድሜ ያገኘኋቸዉ ሴትዮ ለቱናት የተመደበላትን ማደሪያ ክፍል፣ ክፍሉን የሚጋሯትን
ሕጻናት፣ ያለማስታጎል እንዲከታተላት የተመደበላትን ነርስ፣ የምግቦቿን ዝርዝር መርሐ ግብር፣ልብሶቿን እና ሌሎች ነገሮችን በዚያዉ በማይለዋወጥ ትሕትናቸዉ ከገለጹልኝ በኋላ፣ ሥጋት ወይም አስታያየት
ይኖረኝ እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡
“እንግዲያዉ መዋእለ ሕጻናት ብቻ አይደለማ ይኼማ?” አልኋቸዉ:
“ትክክል። ያዉ እንደምታዉቂዉ” አሉ፣ ደጋገሜ አንቺ እንዲሉኝ
የለመንኋቸዉን እንደ ምንም ተስማምተዉልኝ፡ “ያዉ እንደምታዉቂዉ አብዛኛዉ የማኅበራች አገልጋዮች ሌት ከቀ ሥራ ላይ ናቸዉ። በዚህም
የተነሳ ለልጆቻቸዉ በቂ እክብካቤ ለማድረግ ይቸገራሉ። ይኼ የሕጻናት መዋያ ከተከፈተ ወዲህ ግን እንደየአገልግሎት ጸባያቸዉ፣ ሙሉ ኃላፊነቱን ለእኛ ለመተዉ የተፈቀደላቸዉ አገልጋዮች አሉ: ሥራቸዉ ፋታ የሚሰጣቸዉ ያሉ እንደሆነ ግን ኃላፊነት የም ወስድላቸዉ ወይ ቀኑን ወይ ማታዉን ብቻ ይሆናል ማለት ነዉ” አሉኝ፣ ቱናትን ባዘጋጁላት
አልጋዋ ላይ እያሳረፏት፡
“ታዲያ” አልሁኝ፣ ከሁሉም ቅድሚያ ለቱናት የሚበላ እንዲሰጡልኝ ለመጠየቅ እንደገና እየዳዳሁ የአንገት ሰላምታ በርቀት ሰጥተዉኝ ከነበሩት ሴቶች አንደኛዋ፣ የልቤን አዉቃልኝ ይሁን የቱናትን ቡዝዝ ማለት አይታ እንደሆነ እንጃ፣ ትኩስ የሥጋ ፍትፍት አመጣችላት። ደቀቅ
ያለዉን የሥጋ አመታሮ በቀይ እንጀራ ፈትፍታ አምጥታ ስታጎርሳት እኔ ምራቄን ብዉጥም፣ቱናት ግን እምቢ አለች: ለማጫወት ብትሞክራት ሁሉ ለማልቀስ ተነፋነፈች።
“ግድ የለም” አሉ፣ ባልቴቷ። “ግድየለም፤ እንግድነት ተሰምቷት ነዉ። ትንሽ ትፋሽ ትዉሰድና እኔ አጫዉቼ አበላታለሁ”
“አይ አልሁኝ፣ ሥጋቴን መደበቅ እያቃተኝ፡
“ግድ የለሽም”
“እንዲያዉ ዛሬ እምብዛም ሳትበላ ነዉ የዋለችዉ”
“ሐሳብ አይግባሽ፤ አጫዉቼ አበላታለሁ”
“እንግዲህ ምን እላለሁ፣ እግዚአብሔር ይስጥልኝ ከማለት በቀር አልኋቸዉ ኹለቱንም፣ ስለ በጎ አድራጎታቸዉ፡
"ተዪ ተዪ: እኛ ነን ማመስገን ያለብን: እንኳንም እግዚአብሔር ልዩ አድርጎ የሰጠሽ ልጅሽ እንድናገለግላት ዕድሉን ሰጠሸን”
“አይ… እንዲያዉ ወድጄ እንኳን አይደለም ያመጣኋት: ልጄ ከብዳኝ ወይ ደግሞ ከእሷ የሚበልጥብኝ ሥራ ኖሮብኝም አይደለም”
“ይገባኛል”
“የሆነዉ ሆኖ እንግዲህ ከኹለት ወይ ከሦስት ሰዓት በላይ
አላስቸግራችሁም”
“ማስቸገር? የለም የለም: ለእሷ ከምናደርግላት ይልቅ፣ እሷ ለእኛ
የምታደርግልን ይበልጥብናል። ከባሪዎቹ እኛዉ ነን''
“ይሁን” ብዬ፣ ወጣሁ።
ለቅሶዋን ከኋላዬ እየሰማሁ፣ እንደ ምንም ጨክኜ ወጣሁ ወደ ጦር ሜዳ እየኼድሁ እንደሆነ ነዉ የሚሰማኝ፡ ከወንድሞቼ እና
ከእህቶቼ፣ በተለይም ከጃሪም ጋር ፊት ለፊት እስከምገጥም ቸኩያለሁ።እሱም ቢሆን ሌላ ምንም ምርጫ አልተዉልኝም፡፡
‹ምን ይሉት ፍርጃ ነዉ ግን? ኧረ እንደ ዋዛ የት ነዉ የደረስነዉ
በማርያም? እያልሁ እንዲችዉ እንደ ተብሰለሰልሁ፣ በአዲስ አበባ
ዩኒቨርስቲ ዋናዉ ግቢ በኩል ባለዉ ቁልቁለት ወረድሁ።
ለነገሩ ለምን በእነሱ ብቻ እፈርዳለሁ? ጥፋቱ የራሴም ጭምር አይደል?እነሱ ሆኑብኝና ተለማመጥኋቸዉ፡ የእኔ በሕይወት መኖር በእነሱ ፈቃድ እስኪመስል ድረስ ግፊያቸዉን ሁሉ ቻልሁላቸዉ᎓ የጃሪም ወንድምነት
ቢቀርብኝ እሞት ይመስል፣ ያለ ጥፋቴ ጭምር ማረኝ ማረኝ አልሁት።
ቆይ፤ እዉነት ግን አልሞትም? ያለ ጃሪም ወንድምነት፣ ያለ እህቶቼ
እህትነት ምንድን ነኝ እኔ?
ወደ ማኅበራችን ሕንጻ የሚያደርሰኝን መንገድ እንደ ተያያዝሁት፣ የዛፍ እና የንብ ሽርክና በልቡናዬ ክችች አለብኝ፡፡
ሠራተኛዋ ንብ ለማኅበረ ንቧ የሚሆነዉን ምግብ ለመቅሰም አበባ ወዳለው ዛፍ ታርፋለች:: ከአበባዉ ላይ የምታገኘዉን ዕጩ ማር ከቀሰመች በኋላ ተጨማሪ ፍለጋ ወደ ሌላ ባለ አበባ ዛፍ ትሄዳለች: ነገር ግን ከዛፋ
በምትነሳበት ጊዜ፣ የአበባዉ ወንዴ ዘር በጸጉራም አካሏ ላይ ተሳፍሮ ይከተላታል። ወደ ቀጣዩ የአበባ ዛፍ በምታርፍ ጊዜም፣ ያ ከዚያኛዉ ዛፍ ያመጣችዉ ወንዴ ዘር፣ እዚህኛዉ ዘንድ ካለዉ የአበባዉ ሴቴ ዘር ጋር ይገናኛል፡ በዚህም ምክንያት፣ ንቧ ምግቧን ፍለጋ ከዛፍ ዛፍ ባረፈች
ቁጥር፣ የአበባ ዛፎች እንዲራቡ ታደርጋለች ማለት ነዉ ንብ ያለ አበባ ማለት እንግዲህ ያለ ምግብ፤ አበባም ያለ ንብ ማለት ደግሞ ያለ መራባት ስለሆነ ተከላክለዉ አያዉቁም:: እርስ በእርስ ቢከላከሉ፣ አንዳቸዉም መኖር እንደማይችሉ ኹለቱም ጠንቅቀዉ ያዉቁታል።
ስለዚህ ንብ እና አበባ አይለማመኑም:: አለመለማመን ብቻም ሳይሆን፣ ነፍሳቸዉ እስኪገባ ድረስ ይዋደዳሉ
እንደ እዉነቱ፣ እኔና ጃሪምም ሆንን ከሌሎች እህትና ወንድሞቻችንም
ጋር ግን፣ አበባና ንብ ብቻ አይደለንም፡፡ ወይ ንብ እና ንብ፣ ወይ አበባና አበባ ነን፡ ያዉም ወይ የአንድ እናት ንብ እናት አበቦች ነን፡፡ እንዲያዉ እሱም አጉል ሆኖ ቢፈርስ ግን፣ ቢያንስ ንቦች፣ ወይ ደግሞ የአንድ እንደ አበባና ንብ እንኳን መሆን እንዴት ያቅተናል?
የእኔም እጅ አለበት፡፡
አዎ፣ አለበት!
እኔ ያለ እነሱ መኖር እንደማልችል ብቻ እንጂ፣ እነሱም ያለ እኔ መኖር
እንደማይችሉ ነግሪያቸዉ አላዉቅም አበባ የንብን ጥቅም ባያዉቅ ኖሮ አያከብረዉም: የማያከብረዉን ደግሞ የሚወድ የለም፡ መናቅን እንጂ፣በእጄ ነሽ፣ ብለቅሽ ያልቅልሻል፣ ተሸከምሁሽ፣ በደልሽኝ ማለትን እንጂ
እንደ'ኔ ማለትን ያስተዋል፡፡ እህትነቴ እንዲተናነቃቸዉ፣ እነ ጃሪም እዚህ እንዲደርሱ የእኔም ሚና አለበት፡፡
“የት ናት?” አልሁት ባልቻን፣ ከራሴ ጋር እንዲህ እየተዋቀስሁ ወደ
ሲራክ ፯ ማዕከል ደርሼ ቢሮዉ ዉስጥ ያገኘሁት ከኹለት ሰዎች ጋር እየተነጋገረ ቢሆንም፣ ምንም ሳይመስለኝ፡
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
..."ባርባራ ” አለች ሚስዝ ሔር " " የዛሬ ቀን ደስ ማለቱን አየሺው ?”
አዎን በጣም ደስ የሚል ቀን ነው እማማ "
“ ወጣ ብዬ ብመለስ የሚሻለኝ መሳለኝ "
“ በርግጥ ይሻልሻል እማማ !ቶሎ ቶሎ ብትወጭማ ኖሮ ጥቅሙን ታውቂው ነበር ቀኑ እንደ ዛሬ ጥሩ ሲሆን መውጣት ጥሩ ነው ”
“ አባትሽ ከጓሮ አለና እስኪ ይመቸው እንዶሆነ ጠይቂው "
ዳኛው ሔር ከፊት ለፊት የነበረውን አታክልት እየጎበኘ በትእዛዙ መሠረት ያልተሠራውን ለአትክልተኛው ለብንያም ያሳያል " ብንያም ሠረገላ ነጅ የፈሬሶቹ
ባልዶራስ ከመሆኑም ሌላ ከዚያ በሚተርፈው ጊዜም በአትክልተኝነት ይሠራል "
ትዳር አለው ማልዶ በመግባትና አምሽቶ በመጣት ከሠራበት እየተመግበ ! ከራሱ ቤት ይኖራል ጀስቲስ” ሔር ሰው ሠራሽ ጠጉር አጥልቆ የቤት ልብስ ለብሶ
በብንያም እየተቆጣ ሳለ ባርባራ ደረሰች " ከሦስት ልጆቹ ውስጥ አባቷን ደፈር የምትል እሷ ነበረች ሆኖም እንደ ሌሎቹ ባትርበተበትም አጠግቡ ደርሳ በአክብሮት ፍርሃት ቆመች "
“ አባባ ! ”
“ ምን ፈለግሽ ? አላት ግዙፍ ሰውነቱን በማዞር "
እማማ ወጣ ብላ ነፋስ ለመቀበል ትፈልጋለች " ሠረገላ ትፈቅድልናለህ ?”
ዳኛው መልስ ከመስጠቱ በፊት ሰማዩን ቀና ብሎ አየና “ወዴት ለመሔድ ትፈልጋለች ? አለ "
“ ወደ ሱቅ ብቅ ብለን አንዳንድ ነገችን ለመግዛት እንፈልጋለን ከዌስትሊን አንወጣም "
ሚስተር ሔር በሣሩ ውስጥ እየተንጐራደደ ወደ ምግብ ቤቱ ሔደና መስኮቱን ገፋ አድርጐ ከፍቶ ' ' ዛሬ ወደ ሱቅ ለመሔድ ፈለግሽ እንዴ አን ? አላት "
“ እኔ የግድ ዛሬ አላልኩም ” አለችው እየፈራች - “ምን ጊዜም ሊሆን ይችላል " ሠረገላውን የማትፈልገው ከሆነ ግን ፡ቀኑ ሞቃት ስለሆነ ትንሽ ወጣ ብዬ ልመለስ ፈልጌ ነበር " በዚያውም ባርባራ የበጋ ልብሷን ትገዛለች « ”
“ እሷ ሁልጊዜ ልብስ እንደ ገዛች ነው !” ብሎ አጉረመረመ "
“ ኧረ አባባ ! እኔ . . .
ዝም በይ እመቤቲቱ የሚያስፈልግሽ እጥፍ አለሽ ”
“ ምናልባት ሠረገላውን ካልፈቀድክልኝ በእግሬም ቢሆን ቀስ ብዬ ትንሽ ከሔድኩ በኋላ ሲደክመኝ መመለስ እችላለሁ " "
ከዚያ ሳምንት ሙሎ አልጋ ለመያዝ ነው !? በእግር ዌስትሊን ደርሶ መመለስ ? ዕብዶት ነው ” አለና እሺም እምቢም ሳይል መስኮቱን ዘግቶ ወደ ቤንጃሚን ተመለሰ "
" ባርባራ... አባትሽ ሠረገላውን ወዴት ሊሄድበት አስቧል? አለች ሚስስ ሔር
ማንንም መቃወም ዐመል ብሎት ነው እንጂ እሱስ የትም የሚሔድ አይመስለኝም " በእግርሽ መሔድ የምትችይ ይመስለኛልስንመለስ በኪራይ ሰረግላ እንመጣለን።
በርግጥ በእግሬ መሔድ እችላላሁ " አባትሽ ሳይፈቅድ ግን ለመሞከር
አልቃጣውም "
ባርባራ በመስኮት ስትመለከት ቤንጃሚን ያትክልት መሣሪያዎቹን ሰብስቦ አስቀምጦ ጋጦቹ ወደ ነበሩበት ወደ ቤቱ ጀርባ ሲያመራ አየችው " በዚህ ጊዜ በአቋራጭ ሮጣ ቀዶመችውና አባባ በሠረገላ እንድትወስዶን ያዘዘህ ነገር አለ ቤንጃሚን ? ” አለችው "
“ አዎን አንቺንና እሜቴን ዌስትሊን አድርሺ እንድመልሳችሁ ታዝዣለሁ
አላት " እንደገና ተመልሳ የደስ ደሱን ለናቷ ነገረቻት " ከዚያም እህል መሳሪይ አቅርባ ትንሽ አቀመስቻትና ተሣፍረው ሚስተር ሔር በነበረበት በኩል ሲያልፉ ምስጋናዋን በፈግታ ገለጸችላት እሱም “ ልብ በይ ለራት ሰዓት እንድትደርሱ ባርባራ ደግሞ ብዙ ገንዘብ እንዳታጠፉ ተጠንቀቁ ” አላት ከዚያ መንገዳቸውን ቀጠሉ
ዌስትሊን ደርሰው ከሚስተር ካርላይል ቢሮ ፊት ለፊት ከነበረው የጨርቃ ጨርቅ ሱቅ አጠግብ አቁመው ሠረገላውን ከዚያ ትተውት ገቡ "
ከሱቅ ገብተው ሲመርጡ ሲያገላብጡ ' ዋጋ ሲወጋወጉ አንድ ሰዓት ያህል ከቆዩ በኋላ ሚስዝ ሔር ቦርሳዋን አጣችው "
“ ከሠረገላው ውስጥ ትቸው ሳይሆን አይቀርም ... ባርባራ- ሔደሽ ብታመጭልኝሳ የኔ ልጅ ? የሐሩ ናሙናም ከውስጡ ነው ያለው "
ባርባራ ወጥታ ሔደች ሠረገላው ቤንጃሚና ጸጉረ ለስላሳው አሮጌ ፈረስ ፀጥ ብለው ይጠብቃሉ " ባርባራ በዐይኗ ፈልጋ ቦርሳውን ስታጣው አሽከርዮው አዘዘችው።
የእማማን ቦርሳ ፌልገው ቤንጃሚን ከሠረገላው ውስጥ አንዱ ጋ ተወሽቆ ይሆናል።
ቤንጃሚን ከመቀመጫው ወርዶ መፈለግ ጀመረ " ባርባራ በመንግዱ ቁልቁል እየተመለከተች ትጠብቃለች " ፀሐይዋ በጣም ደምቃለች " አንድ ሰውዬ በድንጋይ ንጣፉ መንገድ ይንሸራሸራል " በሰደሪያው የተጋደመው ወፍራም ሰንሰለትና
ከሱ ጋር የተያዙት ልዩ ልዩ ጌጦች hፀሐይዋ ጨረር ጋር ይንቦጋቦጋሉ የሸሚዙ የወርቅ ቁልፎችም ለብቻቸው ያበራሉ " ጓንቲ ባላጠለቀው እጁ ሪዙን ሲያሻሽ የእጁ ንጣት ከሩቅ ይታያል በተለይ ደግሞ ጣቱ ላይ የሰካው ያልማዝ ቀለበት ያንጸባርቃል ባርባራ ወንድሟ ሪቻርድ የነገራትን የዚያን ጌጣጌጥ ወዳድ ሰዬ ነገር ትውስ አላት።
ሲጓዝ ተመለከተችው " ዐይኑና ጸጉሩ ጥቁር ቀጠን ብሎ ረዘም ያለ ዕድው በኻያ ሰባትና ስምንት የሚገመት መልከ መልካም ጐበዝ ነበር ከፍል "ከፍየል ቆዳ የተሠሩ ብጫ ብጤ ጓንቲዎች አንዷን ከግራ እጁ አጥልቋል ሌውን ቀስ ብሎ እያፏጨ በመተከዝ ሲያወዛውዝ አየችው ደማቅ ፀሐይ ባይኖር ኖሮ ባርባራ የወርቁ
ጉጥ አታየውም ወይም ከዚያ አሳዛኝ ምስጢር ጋር በልቧ አታዛምደውም ነበር "
እንዴ ቶርን አንተነህ እንዴ ? እስቲ ወዲህ ተሻገር !
ከመንገድ ወዲያ ማዶ ሆኖ የተናገረው ኦትዌይ ቤተል ሲሆን የተጣራውም ያን በልዩ ልዩ ፈርጥ ያጌጠውን ጎበዝ ነበር » ሰውየው ግን በሐሳብ ተውጦ ስለ አልሰማው እንደገና ጮኽ ብሎ ጠራው ።
“ ካፒቴን ቶርን !
አሁን ሰማውና ራሱን በአዎንታ ነቅንቆ መንገዱን ተሻገረ ባርባራ ሕልም ውስጥ ያለች መሰላት አንጎሏ ' ልቧ ' ሐሳቧ ' አንድ ላይ ተቀላቀሎባት
“ ቦርሳው ይኸውና ሚስ ባርባራ " በሠረግላው የሥጋጃ እጥፋቶች | ውስጥ ገብቶ አገኘሁት " አለና ቤንጃሚን ወደሷ ሲዘረጋላት ልብ አላለችውም » የሆሊጆንን እውነተኛ ገዳይ ማየቷን ያለ ጥርጥር ስለ አረጋገጠች ከዚህ ጉዳይ ውጭ የሆነውን ነገር ሁሉ ረስታዋለች በሁለመናው ሪቻርድ ከነገራት ገለጻ ጋር ተስማማላት"
ረጅም ' በጣም ነጭ ያልሆነ መልከ መልካም ' እጀ ለስላሳ በጌጣ ጌጥ የተንቆጠቆጠና . . . ስሙ ደግሞ ካፒቴን ቶርን ! እሱ ለመሆኑ ምንም አልተጠራጠረችም ፊቷ ባንድ ጊዜ ተለዋወጠ " ልቧ ያለ መጠን ዘለለ
“ ቦርሳው ይኸው ሚስ ባርባራ !” ደገመ ብንጃሚን።
ባርባራ ቤንጃሚንን ከነቦርሳው ጥላው ሔደች » የቀዶ ጥገና ሐኪሙን ሚስተር ዌይንራይትን ከሩቅ አየችውና ወይሱ በረረች
ሚስተር ዌይንራይት . . . ያ ከኦትዌይ ቤተል ጋር የሚነጋግር ሰው ይታይዎታል . . . ማነው ?”
ሚስተር ዌይንራይት ' መልስ ከመስጠቱ በፊት መነጽሩን ከአፍንጫው ቁብ ማድረግ ነበረበት " ምክንያቱም ዐይኑ እሩቅ ነገር አስተካክሎ አያይለትም ነበር «ያ ነው? ካፔቴን ቶርን ይሉታል " የሔርበርትን ቤተሰብ ለማየት የመጣ መሰለኝ "
መኖሪያው የት ነው ? አሁንስ ከየት ነው የመጣው ?
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
..."ባርባራ ” አለች ሚስዝ ሔር " " የዛሬ ቀን ደስ ማለቱን አየሺው ?”
አዎን በጣም ደስ የሚል ቀን ነው እማማ "
“ ወጣ ብዬ ብመለስ የሚሻለኝ መሳለኝ "
“ በርግጥ ይሻልሻል እማማ !ቶሎ ቶሎ ብትወጭማ ኖሮ ጥቅሙን ታውቂው ነበር ቀኑ እንደ ዛሬ ጥሩ ሲሆን መውጣት ጥሩ ነው ”
“ አባትሽ ከጓሮ አለና እስኪ ይመቸው እንዶሆነ ጠይቂው "
ዳኛው ሔር ከፊት ለፊት የነበረውን አታክልት እየጎበኘ በትእዛዙ መሠረት ያልተሠራውን ለአትክልተኛው ለብንያም ያሳያል " ብንያም ሠረገላ ነጅ የፈሬሶቹ
ባልዶራስ ከመሆኑም ሌላ ከዚያ በሚተርፈው ጊዜም በአትክልተኝነት ይሠራል "
ትዳር አለው ማልዶ በመግባትና አምሽቶ በመጣት ከሠራበት እየተመግበ ! ከራሱ ቤት ይኖራል ጀስቲስ” ሔር ሰው ሠራሽ ጠጉር አጥልቆ የቤት ልብስ ለብሶ
በብንያም እየተቆጣ ሳለ ባርባራ ደረሰች " ከሦስት ልጆቹ ውስጥ አባቷን ደፈር የምትል እሷ ነበረች ሆኖም እንደ ሌሎቹ ባትርበተበትም አጠግቡ ደርሳ በአክብሮት ፍርሃት ቆመች "
“ አባባ ! ”
“ ምን ፈለግሽ ? አላት ግዙፍ ሰውነቱን በማዞር "
እማማ ወጣ ብላ ነፋስ ለመቀበል ትፈልጋለች " ሠረገላ ትፈቅድልናለህ ?”
ዳኛው መልስ ከመስጠቱ በፊት ሰማዩን ቀና ብሎ አየና “ወዴት ለመሔድ ትፈልጋለች ? አለ "
“ ወደ ሱቅ ብቅ ብለን አንዳንድ ነገችን ለመግዛት እንፈልጋለን ከዌስትሊን አንወጣም "
ሚስተር ሔር በሣሩ ውስጥ እየተንጐራደደ ወደ ምግብ ቤቱ ሔደና መስኮቱን ገፋ አድርጐ ከፍቶ ' ' ዛሬ ወደ ሱቅ ለመሔድ ፈለግሽ እንዴ አን ? አላት "
“ እኔ የግድ ዛሬ አላልኩም ” አለችው እየፈራች - “ምን ጊዜም ሊሆን ይችላል " ሠረገላውን የማትፈልገው ከሆነ ግን ፡ቀኑ ሞቃት ስለሆነ ትንሽ ወጣ ብዬ ልመለስ ፈልጌ ነበር " በዚያውም ባርባራ የበጋ ልብሷን ትገዛለች « ”
“ እሷ ሁልጊዜ ልብስ እንደ ገዛች ነው !” ብሎ አጉረመረመ "
“ ኧረ አባባ ! እኔ . . .
ዝም በይ እመቤቲቱ የሚያስፈልግሽ እጥፍ አለሽ ”
“ ምናልባት ሠረገላውን ካልፈቀድክልኝ በእግሬም ቢሆን ቀስ ብዬ ትንሽ ከሔድኩ በኋላ ሲደክመኝ መመለስ እችላለሁ " "
ከዚያ ሳምንት ሙሎ አልጋ ለመያዝ ነው !? በእግር ዌስትሊን ደርሶ መመለስ ? ዕብዶት ነው ” አለና እሺም እምቢም ሳይል መስኮቱን ዘግቶ ወደ ቤንጃሚን ተመለሰ "
" ባርባራ... አባትሽ ሠረገላውን ወዴት ሊሄድበት አስቧል? አለች ሚስስ ሔር
ማንንም መቃወም ዐመል ብሎት ነው እንጂ እሱስ የትም የሚሔድ አይመስለኝም " በእግርሽ መሔድ የምትችይ ይመስለኛልስንመለስ በኪራይ ሰረግላ እንመጣለን።
በርግጥ በእግሬ መሔድ እችላላሁ " አባትሽ ሳይፈቅድ ግን ለመሞከር
አልቃጣውም "
ባርባራ በመስኮት ስትመለከት ቤንጃሚን ያትክልት መሣሪያዎቹን ሰብስቦ አስቀምጦ ጋጦቹ ወደ ነበሩበት ወደ ቤቱ ጀርባ ሲያመራ አየችው " በዚህ ጊዜ በአቋራጭ ሮጣ ቀዶመችውና አባባ በሠረገላ እንድትወስዶን ያዘዘህ ነገር አለ ቤንጃሚን ? ” አለችው "
“ አዎን አንቺንና እሜቴን ዌስትሊን አድርሺ እንድመልሳችሁ ታዝዣለሁ
አላት " እንደገና ተመልሳ የደስ ደሱን ለናቷ ነገረቻት " ከዚያም እህል መሳሪይ አቅርባ ትንሽ አቀመስቻትና ተሣፍረው ሚስተር ሔር በነበረበት በኩል ሲያልፉ ምስጋናዋን በፈግታ ገለጸችላት እሱም “ ልብ በይ ለራት ሰዓት እንድትደርሱ ባርባራ ደግሞ ብዙ ገንዘብ እንዳታጠፉ ተጠንቀቁ ” አላት ከዚያ መንገዳቸውን ቀጠሉ
ዌስትሊን ደርሰው ከሚስተር ካርላይል ቢሮ ፊት ለፊት ከነበረው የጨርቃ ጨርቅ ሱቅ አጠግብ አቁመው ሠረገላውን ከዚያ ትተውት ገቡ "
ከሱቅ ገብተው ሲመርጡ ሲያገላብጡ ' ዋጋ ሲወጋወጉ አንድ ሰዓት ያህል ከቆዩ በኋላ ሚስዝ ሔር ቦርሳዋን አጣችው "
“ ከሠረገላው ውስጥ ትቸው ሳይሆን አይቀርም ... ባርባራ- ሔደሽ ብታመጭልኝሳ የኔ ልጅ ? የሐሩ ናሙናም ከውስጡ ነው ያለው "
ባርባራ ወጥታ ሔደች ሠረገላው ቤንጃሚና ጸጉረ ለስላሳው አሮጌ ፈረስ ፀጥ ብለው ይጠብቃሉ " ባርባራ በዐይኗ ፈልጋ ቦርሳውን ስታጣው አሽከርዮው አዘዘችው።
የእማማን ቦርሳ ፌልገው ቤንጃሚን ከሠረገላው ውስጥ አንዱ ጋ ተወሽቆ ይሆናል።
ቤንጃሚን ከመቀመጫው ወርዶ መፈለግ ጀመረ " ባርባራ በመንግዱ ቁልቁል እየተመለከተች ትጠብቃለች " ፀሐይዋ በጣም ደምቃለች " አንድ ሰውዬ በድንጋይ ንጣፉ መንገድ ይንሸራሸራል " በሰደሪያው የተጋደመው ወፍራም ሰንሰለትና
ከሱ ጋር የተያዙት ልዩ ልዩ ጌጦች hፀሐይዋ ጨረር ጋር ይንቦጋቦጋሉ የሸሚዙ የወርቅ ቁልፎችም ለብቻቸው ያበራሉ " ጓንቲ ባላጠለቀው እጁ ሪዙን ሲያሻሽ የእጁ ንጣት ከሩቅ ይታያል በተለይ ደግሞ ጣቱ ላይ የሰካው ያልማዝ ቀለበት ያንጸባርቃል ባርባራ ወንድሟ ሪቻርድ የነገራትን የዚያን ጌጣጌጥ ወዳድ ሰዬ ነገር ትውስ አላት።
ሲጓዝ ተመለከተችው " ዐይኑና ጸጉሩ ጥቁር ቀጠን ብሎ ረዘም ያለ ዕድው በኻያ ሰባትና ስምንት የሚገመት መልከ መልካም ጐበዝ ነበር ከፍል "ከፍየል ቆዳ የተሠሩ ብጫ ብጤ ጓንቲዎች አንዷን ከግራ እጁ አጥልቋል ሌውን ቀስ ብሎ እያፏጨ በመተከዝ ሲያወዛውዝ አየችው ደማቅ ፀሐይ ባይኖር ኖሮ ባርባራ የወርቁ
ጉጥ አታየውም ወይም ከዚያ አሳዛኝ ምስጢር ጋር በልቧ አታዛምደውም ነበር "
እንዴ ቶርን አንተነህ እንዴ ? እስቲ ወዲህ ተሻገር !
ከመንገድ ወዲያ ማዶ ሆኖ የተናገረው ኦትዌይ ቤተል ሲሆን የተጣራውም ያን በልዩ ልዩ ፈርጥ ያጌጠውን ጎበዝ ነበር » ሰውየው ግን በሐሳብ ተውጦ ስለ አልሰማው እንደገና ጮኽ ብሎ ጠራው ።
“ ካፒቴን ቶርን !
አሁን ሰማውና ራሱን በአዎንታ ነቅንቆ መንገዱን ተሻገረ ባርባራ ሕልም ውስጥ ያለች መሰላት አንጎሏ ' ልቧ ' ሐሳቧ ' አንድ ላይ ተቀላቀሎባት
“ ቦርሳው ይኸውና ሚስ ባርባራ " በሠረግላው የሥጋጃ እጥፋቶች | ውስጥ ገብቶ አገኘሁት " አለና ቤንጃሚን ወደሷ ሲዘረጋላት ልብ አላለችውም » የሆሊጆንን እውነተኛ ገዳይ ማየቷን ያለ ጥርጥር ስለ አረጋገጠች ከዚህ ጉዳይ ውጭ የሆነውን ነገር ሁሉ ረስታዋለች በሁለመናው ሪቻርድ ከነገራት ገለጻ ጋር ተስማማላት"
ረጅም ' በጣም ነጭ ያልሆነ መልከ መልካም ' እጀ ለስላሳ በጌጣ ጌጥ የተንቆጠቆጠና . . . ስሙ ደግሞ ካፒቴን ቶርን ! እሱ ለመሆኑ ምንም አልተጠራጠረችም ፊቷ ባንድ ጊዜ ተለዋወጠ " ልቧ ያለ መጠን ዘለለ
“ ቦርሳው ይኸው ሚስ ባርባራ !” ደገመ ብንጃሚን።
ባርባራ ቤንጃሚንን ከነቦርሳው ጥላው ሔደች » የቀዶ ጥገና ሐኪሙን ሚስተር ዌይንራይትን ከሩቅ አየችውና ወይሱ በረረች
ሚስተር ዌይንራይት . . . ያ ከኦትዌይ ቤተል ጋር የሚነጋግር ሰው ይታይዎታል . . . ማነው ?”
ሚስተር ዌይንራይት ' መልስ ከመስጠቱ በፊት መነጽሩን ከአፍንጫው ቁብ ማድረግ ነበረበት " ምክንያቱም ዐይኑ እሩቅ ነገር አስተካክሎ አያይለትም ነበር «ያ ነው? ካፔቴን ቶርን ይሉታል " የሔርበርትን ቤተሰብ ለማየት የመጣ መሰለኝ "
መኖሪያው የት ነው ? አሁንስ ከየት ነው የመጣው ?
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
አንድ ዝናባማ ከሰዓት
ሰማዩ ከብዶ ዝናቡ በጣም እየወረደ ነው: ክፍላችን ውስጥ ያሉ መብራቶች
ሁሉ በርተዋል፡ ቲቪውም እንደተለመደው ተከፍቷል። ክሪስ የመስኮቱን ከባባድ መጋረጃዎች በሁለት እጆቹ ከፈት አድርጎ ይዞ በመቆም ከሩቅ ትንሽ የአሻንጉሊት ባቡር መስሎ ሁልጊዜ አስር ሠዓት ገደማ አሳዛኝ ፊሽካውን እያሰማ የሚያልፈውን ባቡር ለማየት እየጠበቀ ነው:
በራሱ ዓለም ውስጥ ነው፧ እኔም በራሴ አለም ውስጥ እግሮቼን አጣምሬ እኔና
ኬሪ የምንጋራው አልጋ ላይ በመቀመጥ እናታችን ለመጨረሻ የመጣች ጊዜ
ካመጣችው መፅሄት ላይ ምስሎች እየመረጥኩ በውስጡ ያሉትን ፎቶግራፎች በጥንቃቄ እየቆረጥኩ የማልመውን አይነት በደስታ የምኖርበት ቤት፣ ሺ ሴቶችን በጎኑ የሚደርግ ሳይሆን እኔን ብቻ የሚወደኝ የምምኘውን አይነት ረጅም፣ ጠንካራ፣ ጥቁር ፀጉር ያለው ባል በማድረግ የቆራረጥኳቸውን የምስል ቁራጮች ሌላ መፅሀፍ ላይ እየለጠፍኩ ህይወቴን እየሳልኩ ነው።
ዳንሰኛ መሆን ሳቆም ባልና ልጆች ይኖሩኛል የማልመው አይነት ቤት ሲኖረኝ ደግሞ ከውድ ድንጋይ የተሰራ የመታጠቢያ ገንዳ ይኖረኛል ከዚያ ለውበት የሚሆኑ ዘይቶች አደርግበትና ማንም በሩን እያንኳኳ ፈጠን በይ
ሳይለኝ ከፈለግኩ ቀኑን ሙሉ ተዘፍዝፌ እውላለሁ። ከዚያ ቆዳዬ በጣም
ለስላሳና ምንም እንከን የሌለበት ጥርት ያለ ይሆንና ደስ የሚል ሽታ ያለው
የሽቶ ጠረን ይኖረኛል። ይሄ የበሰበሰ አሮጌ ደረቅ እንጨት ሽታና ጣሪያው
ስር ያለው ክፍል አቧራ ከነችግሮቹና አሮጌ እቃዎቹ ጋር እኛን ወጣቶቹን ልክ እንደዚህ አሮጌ ቤት ያለ ጠረን እንዲኖረን አድርጎናል
ክሪስ” አልኩት ጀርባው ላይ እያፈጠጥኩ። “አሁን ጠንካሮች ነን፤ ታዲያ
ለምንድነው እናታችን ተመልሳ እስክትመጣና ሽማግሌው እስኪሞት መጠበቅ ያለብን? ለምንድነው የማምለጫ መንገድ የማንፈልገው?” ቃል አልተነፈሰም። ግን እጆቹ የመጋረጃውን ጨርቅ ጨምድደው ሲይዙ ተመለከትኩ::
“ክሪስ...”
“ስለሱ ማውራት አልፈልግም” አለ በንዴት
“ስለመሄድ እያሰብክ ካልሆነ ታዲያ ለምንድነው እዚያ ቆመህ ባቡሩ እስኪያልፍ የምትጠብቀው?”
“ባቡሩን እየጠበቅኩ አይደለም! በቃ ዝም ብዬ ወደ ውጪ እየተመለከትኩ
ነው:”
በግንባሩ የመስኮቱን መስታወት ተደግፏል። ቅርብ ያለ ጎረቤት እንዲያየው የደፈረ ይመስላል
“ክሪስ ከመስኮቱ ዞር በል የሆነ ሰው ሊያይህ ይችላል”
“ማንም ቢያየኝ ግድ የለኝም!”
የመጀመሪያ ስሜቴ ወደሱ ሮጬ በክንዶቼ አቅፌ ከእናታችን ያጣቸውን
እነዚያን መሳሞች ለማካስ ፊቱን በሙሉ በሚሊየን በሚቆጠሩ መሳሞች
ማዳረስ ነበር እሷ እንደምታደርገው ጭንቅላቱን ደረቴ ላይ አስደግፌ ፀጉሩን እያሻሸሁ በፊት ወደነበረበት አይነት ደስተኛ፣ የሚናደድበት ቀን የሌለው፣ መልካም ነገር ብቻ የሚመለከት ሰው ወደመሆኑ ልመልሰው ፈለግኩ። ነገር ግን በፊት እናታችን ታደርግለት የነበረውን ነገር ሁሉ ባደርግለትም ተመሳሳይ
እንደማይሆን አውቅ ነበር፡ እሷን ነው የሚፈልገው: ተስፋዎቹ፣ ህልሞቹና
እምነቱ በሙሉ በአንዲት ሴት ውስጥ ታሽጓል በእናታችን፡፡
አሁን ከመጣች ሁለት ወር አልፏታል! እዚህ ቤት የምናሳልፈው አንድ ቀን በትክክለኛው ህይወት ሲለካ ከወር በላይ እንደሚረዝም አልገባትም
ስለኛ አትጨነቅም? እንዴት እንደምንኖር አታስብም? ያለምንም ማብራሪያ፣
ምክንያት ወይም ሰበብ ስትተወን እያየ ክሪስ ሁልጊዜ የሷ ቀንደኛ ደጋፊ
እንደሚሆን ታምናለች? ፍቅር በጥርጣሬና በፍርሀት በአንድ ጊዜ ሊፈርስ
እንደሚችልና በፍፁም ዳግመኛ ሊገነባ እንደማይችል አታውቅም?
"ካቲ” አለ ክሪስ ድንገት “የሆነ ቦታ የመሄድ ምርጫ ቢኖርሽ የት ትሄጃለሽ?
“ደቡብ” አልኩ “የሚሞቅና ፀሀያማ የባህር ዳርቻ ወዳለው… ሞገዶች ለስላሳ
ወደሆኑበትና ሀይለኛ ነፋስ ወደማይነፍስበት መሄድ እፈልጋለሁ በነጭ አሸዋ ላይ ጋደም ብዬ የፀሀይ ብርሃኔን እየጠጣሁ ለስለስ ያለ ንፋስ ፀጉሬ ውስጥና ጉንጮቼ ላይ ሲንሸራሸር መስማት ነው የምፈልገው”
“ልክ ነው…” ተስማማ፡ “የገለፅሽበት መንገድ አሪፍ ይመስላል እኔ ግን ልክ
እንደ በረዶ ሸርተቴ ሁሉ በሀይለኛ ሞገድ ውስጥ መንሳፈፍም እወዳለሁ።”
ምስሎቹን እየቆራረጥኩ የነበርኩበትን መቀስና መፅሄቱን አስቀምጬ ሙሉ
በሙሉ ክሪስ ላይ ትኩረት አደረግኩ፡ ክሪስ የሚወዳቸውን ብዙ ስፖርቶች አጥቶ፣ በአንድ ክፍል ውስጥ ታሽጎ፣ ከእድሜው በላይ አርጅቶና አዝኖ ስመለከተው ላፅናናው ብፈልግም እንዴት እንደማፅናናው ግን አላወቅኩም።
ክሪስ እባክህ ከመስኮቱ ጋ ተመለስ?” አልኩት።
“ተይኝ! ይሄ ቦታ እጅግ ሰልችቶኛል ይህንን አታድርግ፣ ያንን አታድርግ፣
ካላናገሩህ እንዳትናገር መባል፤ በየቀኑ እነዚህን በደንብ በደንብ የማይሰሩ ጣዕም አልባ ምግቦች መብላት ታክቶኛል
በምግብም እንኳን እንዳንደሰት ሆነ ብላ ነው እንደዛ የምታደርገው: ስለዛ
ሁሉ ገንዘብ ሳስብ ደግሞ ግማሹ የእናታችንና የእኛ በመሆኑ እንደሚገባን
አስባለሁ። ያ ሽማግሌ መቼም ለዘላለም መኖር አይችልም:"
“በዓለም ላይ ያለ ገንዘብ ሁሉ ቢደመር ያጣናቸውን የመኖሪያ ቀኖች ያህል
ዋጋ የለውም!” በቁጣ መለስኩለት ወደኔ ዞር አለ፤ ፊቱ ቀልቷል። “ምናልባት
አንቺ በተሰጥኦሽ ገንዘብ ታገኚ ይሆናል እኔ ግን ከፊት ለፊቴ የብዙ አመታት
ትምህርት ይጠብቀኛል፡ አባታችን ዶክተር እንድሆን ይጠብቅ እንደነበረ ታውቂያለሽ፡ እንደምንም ብዬ ያንን ማሳካት አለብኝ፡፡ ከዚህ ከኮበለልን ግን
መቼም ዶክተር መሆን አልችልም: አንቺንና መንትዮቹን እንዲሁም ራሴን
ማኖር ይኖርብኛል። እስቲ እኛን ለማኖር ልሰራ የምችላቸውን ስራዎች
ንገሪኝ… ፍጠኚ! ሳህን አጣቢ ወይም ፍራፍሬ ለቃሚ ሌላ ምን መሆን
እችላለሁ? እነዚህ ስራዎችስ የህክምና ትምህርት ቤት ያስገቡኛል?”
የነደደ ቁጣ ሞላኝ፡ እኔ ላደርገው ስለምችለው አስተዋፅኦ ትንሽ እንኳን
ዋጋ አልሰጠውም: “እኔም መስራት እችላለሁ!” አልኩት። “ሁለታችን
ሆነን ማስተዳደር እንችላለን፡ ክሪስ የተራብን ጊዜ አራት የሞቱ አይጦች
ስታመጣልኝ፣ እግዚአብሔር በትልቅ መከራ ጊዜ ለሰዎች ተጨማሪ ጥንካሬና
ችሎታ ይሰጣል ብለኸኝ ነበር፡ እኔም እንደሚሰጥ አምናለሁ: ከዚህ ወጥተን በራሳችን መኖር ስንጀምር በአንድም በሌላም በኩል መንገዳችንን እናስተካክላለን፡ እናም ዶክተር ትሆናለህ! ያንን ዶክተር የሚለውን ማዕረግ
ከስምህ በፊት ለማየት የትኛውንም ነገር አደርጋለሁ፡”
“ምን መስራት ትችያለሽ?" በጥላቻና በመመረር አይነት ጠየቀኝ፡ መልስ መስጠት ከመቻሌ በፊት ከጀርባችን ያለው በር ተhፍቶ አያትየው በሩ ላይ ቆመችና ወደ ክፍሉ ሳትገባ ክሪስ ላይ አፈጠጠች: እሱ ደግሞ እንደበፊቱ ለመታዘዝ ፈቃደኛ ባለመሆን ግትርና እምቢተኛ ሆነና ከመስኮቱ ጋር ሳይንቀሳቀስ ፊቱን መልሶ እንደገና ዝናቡ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለ።
“ልጅ!” ተጣራች። “ከመስኮቱ ጋር ዞር በል አሁኑኑ!
“ስሜ ልጅ አይደለም፧ ስሜ ክሪስቶፈር ነው በተሰጠኝ ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ወይም ጭራሽ አለመጥራት ትችያለሽ ... ግን እንደገና ልጅ ብለሽ እንዳትጠሪኝ፡”
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
አንድ ዝናባማ ከሰዓት
ሰማዩ ከብዶ ዝናቡ በጣም እየወረደ ነው: ክፍላችን ውስጥ ያሉ መብራቶች
ሁሉ በርተዋል፡ ቲቪውም እንደተለመደው ተከፍቷል። ክሪስ የመስኮቱን ከባባድ መጋረጃዎች በሁለት እጆቹ ከፈት አድርጎ ይዞ በመቆም ከሩቅ ትንሽ የአሻንጉሊት ባቡር መስሎ ሁልጊዜ አስር ሠዓት ገደማ አሳዛኝ ፊሽካውን እያሰማ የሚያልፈውን ባቡር ለማየት እየጠበቀ ነው:
በራሱ ዓለም ውስጥ ነው፧ እኔም በራሴ አለም ውስጥ እግሮቼን አጣምሬ እኔና
ኬሪ የምንጋራው አልጋ ላይ በመቀመጥ እናታችን ለመጨረሻ የመጣች ጊዜ
ካመጣችው መፅሄት ላይ ምስሎች እየመረጥኩ በውስጡ ያሉትን ፎቶግራፎች በጥንቃቄ እየቆረጥኩ የማልመውን አይነት በደስታ የምኖርበት ቤት፣ ሺ ሴቶችን በጎኑ የሚደርግ ሳይሆን እኔን ብቻ የሚወደኝ የምምኘውን አይነት ረጅም፣ ጠንካራ፣ ጥቁር ፀጉር ያለው ባል በማድረግ የቆራረጥኳቸውን የምስል ቁራጮች ሌላ መፅሀፍ ላይ እየለጠፍኩ ህይወቴን እየሳልኩ ነው።
ዳንሰኛ መሆን ሳቆም ባልና ልጆች ይኖሩኛል የማልመው አይነት ቤት ሲኖረኝ ደግሞ ከውድ ድንጋይ የተሰራ የመታጠቢያ ገንዳ ይኖረኛል ከዚያ ለውበት የሚሆኑ ዘይቶች አደርግበትና ማንም በሩን እያንኳኳ ፈጠን በይ
ሳይለኝ ከፈለግኩ ቀኑን ሙሉ ተዘፍዝፌ እውላለሁ። ከዚያ ቆዳዬ በጣም
ለስላሳና ምንም እንከን የሌለበት ጥርት ያለ ይሆንና ደስ የሚል ሽታ ያለው
የሽቶ ጠረን ይኖረኛል። ይሄ የበሰበሰ አሮጌ ደረቅ እንጨት ሽታና ጣሪያው
ስር ያለው ክፍል አቧራ ከነችግሮቹና አሮጌ እቃዎቹ ጋር እኛን ወጣቶቹን ልክ እንደዚህ አሮጌ ቤት ያለ ጠረን እንዲኖረን አድርጎናል
ክሪስ” አልኩት ጀርባው ላይ እያፈጠጥኩ። “አሁን ጠንካሮች ነን፤ ታዲያ
ለምንድነው እናታችን ተመልሳ እስክትመጣና ሽማግሌው እስኪሞት መጠበቅ ያለብን? ለምንድነው የማምለጫ መንገድ የማንፈልገው?” ቃል አልተነፈሰም። ግን እጆቹ የመጋረጃውን ጨርቅ ጨምድደው ሲይዙ ተመለከትኩ::
“ክሪስ...”
“ስለሱ ማውራት አልፈልግም” አለ በንዴት
“ስለመሄድ እያሰብክ ካልሆነ ታዲያ ለምንድነው እዚያ ቆመህ ባቡሩ እስኪያልፍ የምትጠብቀው?”
“ባቡሩን እየጠበቅኩ አይደለም! በቃ ዝም ብዬ ወደ ውጪ እየተመለከትኩ
ነው:”
በግንባሩ የመስኮቱን መስታወት ተደግፏል። ቅርብ ያለ ጎረቤት እንዲያየው የደፈረ ይመስላል
“ክሪስ ከመስኮቱ ዞር በል የሆነ ሰው ሊያይህ ይችላል”
“ማንም ቢያየኝ ግድ የለኝም!”
የመጀመሪያ ስሜቴ ወደሱ ሮጬ በክንዶቼ አቅፌ ከእናታችን ያጣቸውን
እነዚያን መሳሞች ለማካስ ፊቱን በሙሉ በሚሊየን በሚቆጠሩ መሳሞች
ማዳረስ ነበር እሷ እንደምታደርገው ጭንቅላቱን ደረቴ ላይ አስደግፌ ፀጉሩን እያሻሸሁ በፊት ወደነበረበት አይነት ደስተኛ፣ የሚናደድበት ቀን የሌለው፣ መልካም ነገር ብቻ የሚመለከት ሰው ወደመሆኑ ልመልሰው ፈለግኩ። ነገር ግን በፊት እናታችን ታደርግለት የነበረውን ነገር ሁሉ ባደርግለትም ተመሳሳይ
እንደማይሆን አውቅ ነበር፡ እሷን ነው የሚፈልገው: ተስፋዎቹ፣ ህልሞቹና
እምነቱ በሙሉ በአንዲት ሴት ውስጥ ታሽጓል በእናታችን፡፡
አሁን ከመጣች ሁለት ወር አልፏታል! እዚህ ቤት የምናሳልፈው አንድ ቀን በትክክለኛው ህይወት ሲለካ ከወር በላይ እንደሚረዝም አልገባትም
ስለኛ አትጨነቅም? እንዴት እንደምንኖር አታስብም? ያለምንም ማብራሪያ፣
ምክንያት ወይም ሰበብ ስትተወን እያየ ክሪስ ሁልጊዜ የሷ ቀንደኛ ደጋፊ
እንደሚሆን ታምናለች? ፍቅር በጥርጣሬና በፍርሀት በአንድ ጊዜ ሊፈርስ
እንደሚችልና በፍፁም ዳግመኛ ሊገነባ እንደማይችል አታውቅም?
"ካቲ” አለ ክሪስ ድንገት “የሆነ ቦታ የመሄድ ምርጫ ቢኖርሽ የት ትሄጃለሽ?
“ደቡብ” አልኩ “የሚሞቅና ፀሀያማ የባህር ዳርቻ ወዳለው… ሞገዶች ለስላሳ
ወደሆኑበትና ሀይለኛ ነፋስ ወደማይነፍስበት መሄድ እፈልጋለሁ በነጭ አሸዋ ላይ ጋደም ብዬ የፀሀይ ብርሃኔን እየጠጣሁ ለስለስ ያለ ንፋስ ፀጉሬ ውስጥና ጉንጮቼ ላይ ሲንሸራሸር መስማት ነው የምፈልገው”
“ልክ ነው…” ተስማማ፡ “የገለፅሽበት መንገድ አሪፍ ይመስላል እኔ ግን ልክ
እንደ በረዶ ሸርተቴ ሁሉ በሀይለኛ ሞገድ ውስጥ መንሳፈፍም እወዳለሁ።”
ምስሎቹን እየቆራረጥኩ የነበርኩበትን መቀስና መፅሄቱን አስቀምጬ ሙሉ
በሙሉ ክሪስ ላይ ትኩረት አደረግኩ፡ ክሪስ የሚወዳቸውን ብዙ ስፖርቶች አጥቶ፣ በአንድ ክፍል ውስጥ ታሽጎ፣ ከእድሜው በላይ አርጅቶና አዝኖ ስመለከተው ላፅናናው ብፈልግም እንዴት እንደማፅናናው ግን አላወቅኩም።
ክሪስ እባክህ ከመስኮቱ ጋ ተመለስ?” አልኩት።
“ተይኝ! ይሄ ቦታ እጅግ ሰልችቶኛል ይህንን አታድርግ፣ ያንን አታድርግ፣
ካላናገሩህ እንዳትናገር መባል፤ በየቀኑ እነዚህን በደንብ በደንብ የማይሰሩ ጣዕም አልባ ምግቦች መብላት ታክቶኛል
በምግብም እንኳን እንዳንደሰት ሆነ ብላ ነው እንደዛ የምታደርገው: ስለዛ
ሁሉ ገንዘብ ሳስብ ደግሞ ግማሹ የእናታችንና የእኛ በመሆኑ እንደሚገባን
አስባለሁ። ያ ሽማግሌ መቼም ለዘላለም መኖር አይችልም:"
“በዓለም ላይ ያለ ገንዘብ ሁሉ ቢደመር ያጣናቸውን የመኖሪያ ቀኖች ያህል
ዋጋ የለውም!” በቁጣ መለስኩለት ወደኔ ዞር አለ፤ ፊቱ ቀልቷል። “ምናልባት
አንቺ በተሰጥኦሽ ገንዘብ ታገኚ ይሆናል እኔ ግን ከፊት ለፊቴ የብዙ አመታት
ትምህርት ይጠብቀኛል፡ አባታችን ዶክተር እንድሆን ይጠብቅ እንደነበረ ታውቂያለሽ፡ እንደምንም ብዬ ያንን ማሳካት አለብኝ፡፡ ከዚህ ከኮበለልን ግን
መቼም ዶክተር መሆን አልችልም: አንቺንና መንትዮቹን እንዲሁም ራሴን
ማኖር ይኖርብኛል። እስቲ እኛን ለማኖር ልሰራ የምችላቸውን ስራዎች
ንገሪኝ… ፍጠኚ! ሳህን አጣቢ ወይም ፍራፍሬ ለቃሚ ሌላ ምን መሆን
እችላለሁ? እነዚህ ስራዎችስ የህክምና ትምህርት ቤት ያስገቡኛል?”
የነደደ ቁጣ ሞላኝ፡ እኔ ላደርገው ስለምችለው አስተዋፅኦ ትንሽ እንኳን
ዋጋ አልሰጠውም: “እኔም መስራት እችላለሁ!” አልኩት። “ሁለታችን
ሆነን ማስተዳደር እንችላለን፡ ክሪስ የተራብን ጊዜ አራት የሞቱ አይጦች
ስታመጣልኝ፣ እግዚአብሔር በትልቅ መከራ ጊዜ ለሰዎች ተጨማሪ ጥንካሬና
ችሎታ ይሰጣል ብለኸኝ ነበር፡ እኔም እንደሚሰጥ አምናለሁ: ከዚህ ወጥተን በራሳችን መኖር ስንጀምር በአንድም በሌላም በኩል መንገዳችንን እናስተካክላለን፡ እናም ዶክተር ትሆናለህ! ያንን ዶክተር የሚለውን ማዕረግ
ከስምህ በፊት ለማየት የትኛውንም ነገር አደርጋለሁ፡”
“ምን መስራት ትችያለሽ?" በጥላቻና በመመረር አይነት ጠየቀኝ፡ መልስ መስጠት ከመቻሌ በፊት ከጀርባችን ያለው በር ተhፍቶ አያትየው በሩ ላይ ቆመችና ወደ ክፍሉ ሳትገባ ክሪስ ላይ አፈጠጠች: እሱ ደግሞ እንደበፊቱ ለመታዘዝ ፈቃደኛ ባለመሆን ግትርና እምቢተኛ ሆነና ከመስኮቱ ጋር ሳይንቀሳቀስ ፊቱን መልሶ እንደገና ዝናቡ ላይ ማፍጠጥ ቀጠለ።
“ልጅ!” ተጣራች። “ከመስኮቱ ጋር ዞር በል አሁኑኑ!
“ስሜ ልጅ አይደለም፧ ስሜ ክሪስቶፈር ነው በተሰጠኝ ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ወይም ጭራሽ አለመጥራት ትችያለሽ ... ግን እንደገና ልጅ ብለሽ እንዳትጠሪኝ፡”
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
‹‹አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ግድ የለኝም፡፡ ጦርነት አውድማ ውስጥ ገብቼ ፋሺዝምን ከሀገሬ ለማባረር እዋጋለሁ›› አለች በልበ ሙሉነት፡ ፊቷ ላይ
የሚነበበው ገፅታ ለህይወት ግድ እንደሌላት ያሳያል፡ ሄሪ ይህን ሲያይ ጎበዝ ናት› አለ በሆዱ፡፡
‹‹የቆረጥሽ ትመስያለሽ››
‹‹በዚህ እምነቱ የተነሳ የስፔን ፋሺስቶችን ሊዋጋ ሄዶ አፈር በልቶ የቀረ ፍቅረኛ ነበረኝ፡፡ የእሱን አርማ አንስቼ አላማውን ዳር ለማድረስ እታገላለሁ››ደ አለች በወኔና በሀዘን፡
‹‹ትወጂው ነበር?»
በአዎንታ ራሷን ነቀነቀች፡፡
አይኗ እንባ እንዳቀረረ ተመለከተና በሀዘኔታ ክንዷን ያዝ አደረጋት
‹‹አሁንም ትወጂዋለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ጊዜም ከልቤ አይጠፋም›› አለች የሹክሹክታ ያህል ‹‹ስሙ ኢያን ይባላል፡››
ሄሪ አሳዘነችው፡፡ ማርጋሬትን ደረቱ ውስጥ ወሽቆ ሊያፅናናት
ቢፈልግም በየት በኩል። ውስኪያቸውን እየጨለጡ ጋዜጣ የሚያነቡ በርበሬ
ፊት አባቷ ፊት ለፊት ተቀምጠዋል፡ እንደ ምንም እጁን ሰደደና አጇን ጨመቅ አደረገው፡፡ እሷም ለማፅናናት መሆኑ ገብቷት
ፈገግ አለች።
‹‹እራት ደርሷል ሚስተር ቫንዴርፖስት›› አለ አስተናጋጁ፡ ሄሪ አስራ
ሁለት ሰዓት ከምኔው እንደደረሰ ገርሞታል፡ ከማርጋሬት ጋር የጀመረውን
ጭውውት ማቋረጡ አሳዝኖታል፡፡ እሷም የእሱ ጭንቀት ገባትና ‹ብዙ
የምንጫወተው ነገር አለ›› አለች ‹‹ለሚቀጥሉት ሃያ አራት ሰዓታት አብረን
እንሆናለን››
‹‹ልክ ነሽ›› አለና ፈገግ አለ፡፡ እንደገና እጇን ዳበስ አደረገና ‹‹በኋላ
እንገናኝ›› አላት፡፡
ምስጢሩን በሙሉ የነገራት አጋሩ ሊያደርጋት ነው፡፡
ወደሚቀጥለው ክፍል ሲገባ ክፍሉ ከሳሎን ቤት ወደ መብል ቤትነት ተለውጦ ሲያይ ተገረመ እያንዳንዳቸው አራት ሰዎች የሚቀመጡባቸው
ሶስት ጠረጴዛዎች የተዘረጉ ሲሆን ሌሎች ሁለት ትንንሽ ጠረጴዛዎችም ይታያሉ፡፡ የእቃው አደራደር እንደ ምግብ ቤት ሲሆን ጠረጴዛዎቹ ጨርቅ
ለብሰዋል፡፡ በላያቸው ላይ የፓን አሜሪካ አየር መንገድ ስምና ምልክት ያለባቸው ብርጭቆዎች፣ ሰሃኖችና ናፕኪኖች ተቀምጠዋል። የመብል ክፍሉ ግርግዳ የአለም ካርታ ተለጥፎበታል አስተናጋጁ ሄሪን አንድ ሱፍ የለበሰ አጠርና ደልደል ካለ ሰው አጠገብ ወስዶ አስቀመጠው: ሄሪ የሰውዬው አለባበስ አስቀናው፡ ሰውዬው ክራቫት ያደረገ ሲሆን ውድ በሆነ ማያያዣ ጌጥ ከሸሚዙ ጋር አያይዞታል፡ ሄሪ እራሱን አስተዋወቀ፡ ሰውዬውም እጁን ለሰላምታ ዘረጋና ‹ቶም ሉተር እባላለሁ›› አለ፡፡ እጁ ላይ ያለው የወርቅ አምባር ከክራቫት ማያያዣው ጋር ይሄዳል፡፡ ለውድ ጌጣጌጥ ገንዘቡን
መበተን የሚወድ ሰው ማለት ይሄ ነው፡፡
ሄሪ የታጠፈውን ናፕኪን ዘረጋ፡፡ ሉተር አነጋገሩ የአሜሪካዊ ነው።
‹‹ከየት ሀገር ነው የመጣኸው?›› ሲል ሄሪ ጠየቀው ሰውዬውን
‹‹ፕሮቪደንስ ሮድ አይላንድ፧ አንተስ?››
‹‹ፊላደልፊያ›› አለ ሄሪ፡ ፊላደልፊያ የት እንዳለ እንኳን አያውቅም፡፡
አሜሪካ ውስጥ ያልኖርኩበት ቦታ የለም፡፡ አባቴ የኢንሹራንስ ሰራተኛ
ነበር፡››
ሉተር አንገቱን ነቀነቀ፡፡ ነገር ግን ከዚህ በላይ ማውራት አልፈለገም የሰውዬው ዝምተኛነት ለሄሪ ተስማምቶታል፡ ስለአኗኗሩ ሰው እንዲጠይቀው
አይፈልግም: በዝምታ ማለፍ ጥሩ ነው፡
ሁለት የአይሮፕላኑ ሰራተኞች በመጡና ራሳቸውን አስተዋወቁ፡ የበረራዐመሀንዲሱ ኤዲ ዲኪን ትከሻው የሰፋ፣ የደስ ደስ ያለው ፀጉረ ነጭ ሰው
ነው፡ ሁለተኛው ጃክ አሽፎርድ የሚባል ናቪጌተር ነው ፀጉረ ጥቁር ሲሆን
የለበሰው ዩኒፎርም ሄዶበታል።
ሰዎቹ እንደተቀመጡ በሉተርና በመሃንዲሱ መካከል የሆነ ጠብ እንዳለ
ሄሪ አስተዋለ።እራት ቀረበ፤ ሁለቱ የአይሮፕላን ሰራተኞች ኮካ ኮላ ሲመጣላቸው ሄሪ
ነጭ ቪኖ ቀረበለት፡ ቶምሉተር ማርቲኒ አዘዘ
ሄሪ እራት እየበላ ሳ
በአይሮፕላኑ መስኮት እያየ ስለማርጋሬትና ስፔን
ሄዶ ስለቀረው ቦይ ፍሬንዷ ያስባል፡፡ ስለእሱ አሁን ምን ያህል እንደምታስብ ማወቅ ፈለገ፡፡ ከእሷ እድሜ አንጻር አንድ አመት ትንሽ ጊዜ አይደለም፡፡
ጃክ አሽፎርድ ሄሪ በመስኮት እያየ መሆኑን ተገነዘበና ‹‹እስካሁን አየሩ
ጥሩ ስለሆነ እድለኞች ነን›› አለ፡
‹‹ሁልጊዜ እንዴት ነው አየሩ?›› ሲል ጠየቀ ሄሪ
‹‹አንዳንድ ጊዜ ከአየርላንድ እስከ ካናዳ በዝናብ የምንሄድበት ጊዜ አለ፡፡
‹‹አንዳንዴ ደግሞ በረዶና መብረቅ ያጋጥማል፡››
ሄሪ አንድ ጊዜ ያነበበውን አስታወሰና ‹‹በረዶ ከዘነበ ለአይሮፕላኑ አደገኛ አይደለም?›› ሲል ጠየቀ፡
‹‹በተቻለን መጠን ቀዝቃዛው የአየር ንብረት እንዳያገኘን እንጥራለን፡፡ለማንኛውም ተብሎ ግን አይሮፕላኑ ክንፎች ላይ የበረዶ ማቅለጫ ሸራ
ተደርጎለታል፡››
የመጪው የአየር ትንበያ ምን ያመለክታል?››
ጃክ ይህን መልስ ለመስጠት ሲጠራጠር አየና ስለአየሩ ባልጠየቅ ይሻል
ነበር›› ሲል አሰበ፡፡ ‹‹አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ዶፍ ዝናብ ይጠብቀናል››
አለ፡፡
‹‹ይህን ያህል መጥፎ ነው?›› ጠየቀ ሄሪ፡
‹‹ዶፍ ዝናቡ መሃል ከገባን መጥፎ ነው፡ ሆኖም እኛ ከዶፍ ዝናቡ ራቅ ብለን እንበራለን›› አለ በሰጠው መልስ ብዙም ባለመተማመን፡፡
ቶም ሉተርም ቀጠለና ‹በዶፍ ዝናብ ውስጥ መጓዝ ምን ችግር አለው ሲል ጠየቀ።
ጃክ በዝርዝር አልተናገረም፤ ነገር ግን የበረራ መሀንዲሱ ኤዲ፣ ቶም ሉተርን ለማስፈራራት ሲል ወደ እሱ እያየ ‹‹ልክ ባልተገራ ፈረስ የሚጋልቡ ይመስል ያነጥራል›› አለ፡
ሉተር ኤዲ ያለውን ሲሰማ በድንጋጤ አመድ መሰለ፡፡ ኤዲ በተሳፋሪው
ፊት አፉ እንዳመጣ በመናገሩ ጃክ ገላመጠው:
ተሳፋሪዎቹ ሁለተኛ ዙር የእንቁራሪት መረቅ መጣላቸው:🤮
አሁን የሚያስተናግዱት ሁለቱ አስተናጋጆች ኒኪና ዴቪ ናቸው፡ ኒኪ ድብልብል ሲሆን ዴቪ ደግሞ ከአፍ የወደቀች ጥሬ ነው የሚያክለው፡፡
ሄሪ ሁለቱም ወንዳገረዶች ሳይሆኑ አይቀሩም› ሲል ገመተ፡ ታዲያ ቅልጥፍናው አስደስቶታል፡፡
ሄሪ በድብቅ እንደተከታተለው የበረራ መሀንዲሱ አዕምሮው በአንድ ነገር የተጠመደ ይመስላል፡፡
‹ሄሪ መሀንዲሱ ባህሪው አኩራፊ አይመስልም፡፡ ሲያዩት ተጫዋችና
ግልፅ ይመስላል› ሲል አሰበና እንዲናገር ለማበረታት ‹‹አንተ ምግብ በምትበላበት ጊዜ የበረራ ምህንድስናውን ስራ ማን ይሰራል?›› ሲል ጠየቀው
‹‹ረዳት የበረራ መሀንዲሱ ሚኪ ፊን ነው›› አለ፡ ‹‹በፈረቃ ነው የምንሰራው፡፡ ጃክና እኔ ከሳውዝ ሃምፕተን በረራ ከጀመርንበት ከቀኑ
ስምንት ሰዓት ጀምሮ ስንሰራ ቆይተናል፡፡ ስለዚህ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት
ላይ እረፍት እናደርጋለን፡፡››
‹‹ካፒቴኑስ?›› ሲል ጠየቀ ቶም ሉተር ሀሳብ ገብቶት።
‹‹እንቅልፍ እንዳይዘው መድሃኒት ይውጣል፡ ከቻለ በተቀመጠበት ትንሽ ያንቀላፋል›› አለ ኤዲ፡ ‹‹ወደኋላ የማንመለስበት ሁኔታ ላይ ስንደርስ
ፓይለቱ ምን አልባት ረጅም እረፍት ያደርጋል፡››
‹‹ስለዚህ በሰማይ በምንበርበት ጊዜ ፓይለቱ ይተኛል ማለት ነው?››
ሲል ጠየቀ ሉተር ሳያስበው ጮክ ብሎ፡
‹‹አዎ›› አለ ኤዲ በፈገግታ:፡ ሉተር ፍርሃት ፍርሃት እንዳለው ያስታውቅበታል፡፡ ሄሪ ጨዋታው ሰላማዊ እንደሆነ በማሰብ ‹‹ወደኋላ
የማንመለስበት ሁኔታ ማለት ምንድን ነው?›› ሲል ጠየቀ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
‹‹አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ግድ የለኝም፡፡ ጦርነት አውድማ ውስጥ ገብቼ ፋሺዝምን ከሀገሬ ለማባረር እዋጋለሁ›› አለች በልበ ሙሉነት፡ ፊቷ ላይ
የሚነበበው ገፅታ ለህይወት ግድ እንደሌላት ያሳያል፡ ሄሪ ይህን ሲያይ ጎበዝ ናት› አለ በሆዱ፡፡
‹‹የቆረጥሽ ትመስያለሽ››
‹‹በዚህ እምነቱ የተነሳ የስፔን ፋሺስቶችን ሊዋጋ ሄዶ አፈር በልቶ የቀረ ፍቅረኛ ነበረኝ፡፡ የእሱን አርማ አንስቼ አላማውን ዳር ለማድረስ እታገላለሁ››ደ አለች በወኔና በሀዘን፡
‹‹ትወጂው ነበር?»
በአዎንታ ራሷን ነቀነቀች፡፡
አይኗ እንባ እንዳቀረረ ተመለከተና በሀዘኔታ ክንዷን ያዝ አደረጋት
‹‹አሁንም ትወጂዋለሽ?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ጊዜም ከልቤ አይጠፋም›› አለች የሹክሹክታ ያህል ‹‹ስሙ ኢያን ይባላል፡››
ሄሪ አሳዘነችው፡፡ ማርጋሬትን ደረቱ ውስጥ ወሽቆ ሊያፅናናት
ቢፈልግም በየት በኩል። ውስኪያቸውን እየጨለጡ ጋዜጣ የሚያነቡ በርበሬ
ፊት አባቷ ፊት ለፊት ተቀምጠዋል፡ እንደ ምንም እጁን ሰደደና አጇን ጨመቅ አደረገው፡፡ እሷም ለማፅናናት መሆኑ ገብቷት
ፈገግ አለች።
‹‹እራት ደርሷል ሚስተር ቫንዴርፖስት›› አለ አስተናጋጁ፡ ሄሪ አስራ
ሁለት ሰዓት ከምኔው እንደደረሰ ገርሞታል፡ ከማርጋሬት ጋር የጀመረውን
ጭውውት ማቋረጡ አሳዝኖታል፡፡ እሷም የእሱ ጭንቀት ገባትና ‹ብዙ
የምንጫወተው ነገር አለ›› አለች ‹‹ለሚቀጥሉት ሃያ አራት ሰዓታት አብረን
እንሆናለን››
‹‹ልክ ነሽ›› አለና ፈገግ አለ፡፡ እንደገና እጇን ዳበስ አደረገና ‹‹በኋላ
እንገናኝ›› አላት፡፡
ምስጢሩን በሙሉ የነገራት አጋሩ ሊያደርጋት ነው፡፡
ወደሚቀጥለው ክፍል ሲገባ ክፍሉ ከሳሎን ቤት ወደ መብል ቤትነት ተለውጦ ሲያይ ተገረመ እያንዳንዳቸው አራት ሰዎች የሚቀመጡባቸው
ሶስት ጠረጴዛዎች የተዘረጉ ሲሆን ሌሎች ሁለት ትንንሽ ጠረጴዛዎችም ይታያሉ፡፡ የእቃው አደራደር እንደ ምግብ ቤት ሲሆን ጠረጴዛዎቹ ጨርቅ
ለብሰዋል፡፡ በላያቸው ላይ የፓን አሜሪካ አየር መንገድ ስምና ምልክት ያለባቸው ብርጭቆዎች፣ ሰሃኖችና ናፕኪኖች ተቀምጠዋል። የመብል ክፍሉ ግርግዳ የአለም ካርታ ተለጥፎበታል አስተናጋጁ ሄሪን አንድ ሱፍ የለበሰ አጠርና ደልደል ካለ ሰው አጠገብ ወስዶ አስቀመጠው: ሄሪ የሰውዬው አለባበስ አስቀናው፡ ሰውዬው ክራቫት ያደረገ ሲሆን ውድ በሆነ ማያያዣ ጌጥ ከሸሚዙ ጋር አያይዞታል፡ ሄሪ እራሱን አስተዋወቀ፡ ሰውዬውም እጁን ለሰላምታ ዘረጋና ‹ቶም ሉተር እባላለሁ›› አለ፡፡ እጁ ላይ ያለው የወርቅ አምባር ከክራቫት ማያያዣው ጋር ይሄዳል፡፡ ለውድ ጌጣጌጥ ገንዘቡን
መበተን የሚወድ ሰው ማለት ይሄ ነው፡፡
ሄሪ የታጠፈውን ናፕኪን ዘረጋ፡፡ ሉተር አነጋገሩ የአሜሪካዊ ነው።
‹‹ከየት ሀገር ነው የመጣኸው?›› ሲል ሄሪ ጠየቀው ሰውዬውን
‹‹ፕሮቪደንስ ሮድ አይላንድ፧ አንተስ?››
‹‹ፊላደልፊያ›› አለ ሄሪ፡ ፊላደልፊያ የት እንዳለ እንኳን አያውቅም፡፡
አሜሪካ ውስጥ ያልኖርኩበት ቦታ የለም፡፡ አባቴ የኢንሹራንስ ሰራተኛ
ነበር፡››
ሉተር አንገቱን ነቀነቀ፡፡ ነገር ግን ከዚህ በላይ ማውራት አልፈለገም የሰውዬው ዝምተኛነት ለሄሪ ተስማምቶታል፡ ስለአኗኗሩ ሰው እንዲጠይቀው
አይፈልግም: በዝምታ ማለፍ ጥሩ ነው፡
ሁለት የአይሮፕላኑ ሰራተኞች በመጡና ራሳቸውን አስተዋወቁ፡ የበረራዐመሀንዲሱ ኤዲ ዲኪን ትከሻው የሰፋ፣ የደስ ደስ ያለው ፀጉረ ነጭ ሰው
ነው፡ ሁለተኛው ጃክ አሽፎርድ የሚባል ናቪጌተር ነው ፀጉረ ጥቁር ሲሆን
የለበሰው ዩኒፎርም ሄዶበታል።
ሰዎቹ እንደተቀመጡ በሉተርና በመሃንዲሱ መካከል የሆነ ጠብ እንዳለ
ሄሪ አስተዋለ።እራት ቀረበ፤ ሁለቱ የአይሮፕላን ሰራተኞች ኮካ ኮላ ሲመጣላቸው ሄሪ
ነጭ ቪኖ ቀረበለት፡ ቶምሉተር ማርቲኒ አዘዘ
ሄሪ እራት እየበላ ሳ
በአይሮፕላኑ መስኮት እያየ ስለማርጋሬትና ስፔን
ሄዶ ስለቀረው ቦይ ፍሬንዷ ያስባል፡፡ ስለእሱ አሁን ምን ያህል እንደምታስብ ማወቅ ፈለገ፡፡ ከእሷ እድሜ አንጻር አንድ አመት ትንሽ ጊዜ አይደለም፡፡
ጃክ አሽፎርድ ሄሪ በመስኮት እያየ መሆኑን ተገነዘበና ‹‹እስካሁን አየሩ
ጥሩ ስለሆነ እድለኞች ነን›› አለ፡
‹‹ሁልጊዜ እንዴት ነው አየሩ?›› ሲል ጠየቀ ሄሪ
‹‹አንዳንድ ጊዜ ከአየርላንድ እስከ ካናዳ በዝናብ የምንሄድበት ጊዜ አለ፡፡
‹‹አንዳንዴ ደግሞ በረዶና መብረቅ ያጋጥማል፡››
ሄሪ አንድ ጊዜ ያነበበውን አስታወሰና ‹‹በረዶ ከዘነበ ለአይሮፕላኑ አደገኛ አይደለም?›› ሲል ጠየቀ፡
‹‹በተቻለን መጠን ቀዝቃዛው የአየር ንብረት እንዳያገኘን እንጥራለን፡፡ለማንኛውም ተብሎ ግን አይሮፕላኑ ክንፎች ላይ የበረዶ ማቅለጫ ሸራ
ተደርጎለታል፡››
የመጪው የአየር ትንበያ ምን ያመለክታል?››
ጃክ ይህን መልስ ለመስጠት ሲጠራጠር አየና ስለአየሩ ባልጠየቅ ይሻል
ነበር›› ሲል አሰበ፡፡ ‹‹አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ዶፍ ዝናብ ይጠብቀናል››
አለ፡፡
‹‹ይህን ያህል መጥፎ ነው?›› ጠየቀ ሄሪ፡
‹‹ዶፍ ዝናቡ መሃል ከገባን መጥፎ ነው፡ ሆኖም እኛ ከዶፍ ዝናቡ ራቅ ብለን እንበራለን›› አለ በሰጠው መልስ ብዙም ባለመተማመን፡፡
ቶም ሉተርም ቀጠለና ‹በዶፍ ዝናብ ውስጥ መጓዝ ምን ችግር አለው ሲል ጠየቀ።
ጃክ በዝርዝር አልተናገረም፤ ነገር ግን የበረራ መሀንዲሱ ኤዲ፣ ቶም ሉተርን ለማስፈራራት ሲል ወደ እሱ እያየ ‹‹ልክ ባልተገራ ፈረስ የሚጋልቡ ይመስል ያነጥራል›› አለ፡
ሉተር ኤዲ ያለውን ሲሰማ በድንጋጤ አመድ መሰለ፡፡ ኤዲ በተሳፋሪው
ፊት አፉ እንዳመጣ በመናገሩ ጃክ ገላመጠው:
ተሳፋሪዎቹ ሁለተኛ ዙር የእንቁራሪት መረቅ መጣላቸው:🤮
አሁን የሚያስተናግዱት ሁለቱ አስተናጋጆች ኒኪና ዴቪ ናቸው፡ ኒኪ ድብልብል ሲሆን ዴቪ ደግሞ ከአፍ የወደቀች ጥሬ ነው የሚያክለው፡፡
ሄሪ ሁለቱም ወንዳገረዶች ሳይሆኑ አይቀሩም› ሲል ገመተ፡ ታዲያ ቅልጥፍናው አስደስቶታል፡፡
ሄሪ በድብቅ እንደተከታተለው የበረራ መሀንዲሱ አዕምሮው በአንድ ነገር የተጠመደ ይመስላል፡፡
‹ሄሪ መሀንዲሱ ባህሪው አኩራፊ አይመስልም፡፡ ሲያዩት ተጫዋችና
ግልፅ ይመስላል› ሲል አሰበና እንዲናገር ለማበረታት ‹‹አንተ ምግብ በምትበላበት ጊዜ የበረራ ምህንድስናውን ስራ ማን ይሰራል?›› ሲል ጠየቀው
‹‹ረዳት የበረራ መሀንዲሱ ሚኪ ፊን ነው›› አለ፡ ‹‹በፈረቃ ነው የምንሰራው፡፡ ጃክና እኔ ከሳውዝ ሃምፕተን በረራ ከጀመርንበት ከቀኑ
ስምንት ሰዓት ጀምሮ ስንሰራ ቆይተናል፡፡ ስለዚህ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት
ላይ እረፍት እናደርጋለን፡፡››
‹‹ካፒቴኑስ?›› ሲል ጠየቀ ቶም ሉተር ሀሳብ ገብቶት።
‹‹እንቅልፍ እንዳይዘው መድሃኒት ይውጣል፡ ከቻለ በተቀመጠበት ትንሽ ያንቀላፋል›› አለ ኤዲ፡ ‹‹ወደኋላ የማንመለስበት ሁኔታ ላይ ስንደርስ
ፓይለቱ ምን አልባት ረጅም እረፍት ያደርጋል፡››
‹‹ስለዚህ በሰማይ በምንበርበት ጊዜ ፓይለቱ ይተኛል ማለት ነው?››
ሲል ጠየቀ ሉተር ሳያስበው ጮክ ብሎ፡
‹‹አዎ›› አለ ኤዲ በፈገግታ:፡ ሉተር ፍርሃት ፍርሃት እንዳለው ያስታውቅበታል፡፡ ሄሪ ጨዋታው ሰላማዊ እንደሆነ በማሰብ ‹‹ወደኋላ
የማንመለስበት ሁኔታ ማለት ምንድን ነው?›› ሲል ጠየቀ፡፡
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ብጠጣለት የሚጎዳኝ ይመስልሃል?"
ወራጅ ውሃ እኮ ነው። እፅዋት በልምላሜ ፈክተው ጎንበስ ቀና እያሉ የሚወዛወዙበት አራዊት እየፈነደቁ የሚፈነጥዙበት
ዋኔ ዳክዬዎች ብቅ ጥልቅ እያሉ ተጎንጭተው የሚንሳፈፉበት ወደ
ሰማዬ ሰማያት ጉነው የሚበሩበት... ውሃ የሚጎዳሽ አይመስለኝም፡፡
ስለዚህ ይህን ከብክለት ነፃ የሆነ ውሃ በእጆችሽ መዳፍ እያፈሰሽ ተጎጭው ማሬ አላት፡፡
ኮንችት እድሜዋ ባጠረ ግርምታ ተመሰከተችውና፡-
“ይገባኛል ገና አልተበከለም ገና አልቆሸሽም… ስልጣኔ
ኩሉን አልጣላበትም ቅርሻቱን አልደፋበትም… በእርግጥ ሳልፈራ መጠጣት ነበረብኝ ብላ በርከክ ብላ ሁለት እጆችዋን እንደ አካፋ አሹላ በእፍኝዋ የቀዳችውን ውሃ እንደ ወፎቹ አንጋጣ ወደ ጉሮሮዋ
አንቀረቆረችው፡ ጎርፍ መሳዩ ንፁህ ውሃ ጉሮሮዋን እያቀዘቀዛት ቁልቁል ወረደ ደስ አላት ጣማት፡፡ ስለዚህ እየደጋገመች ተጎነጨችው፡፡
ቀና ብላ አየች ሰማያዊው ሰማይ ተውቧል ! ወደ ዳርና
ዳር እፅዋትን ተመለከተች የቆላ ዋንዛ፡ ጥቁር እንጨት እንኮይ ጠዪ. ቃጫ. . . በአረንጓዴ ልምላሜ ተሞልተው ምድሯን
አስውበዋታል፡ ጉጉት ድርጭት ጂግራ ቆቅ… ወፎች ይዘምራሉ ይጯሀሉ ይስቃሉ… አቦ ሽማኔ አንበሳው ቆርኪው ዝንጀሮው ጦጣና ጉሬዛው. በእዕዋት ስር ሲርመሰመሱ፡ በእዕዋት ቅርንጫፎች
ላይ እየተንጨዋለሉ ሲወናጨፉ ይታያሉ፡፡
እባቡ እንሽላሊቱ… በዕፅዋት ግንድ
ይልወሰወሳሉ፡፡ ኦሞ ወንዝ ላይ አዞው ራሱን አውጥቶ ይንሳፈፋል፧አሶች ብቅ እያሉ ጥቡሉቅ ይላሉ….
ተፈጥሮ እንደ ሙሽራ ደምቃለች አምራለች ፈክታለች...እንደ ማራኪው የአዳም ዘመን ገነት ኑሮ! ኮንችት ያን ድንቅ ውበት
በአይኗ በጆሮዋ ባጠቃላይ በስሜት ሕዋሶችዋ እየኮረሻሽመች በላችው እንዳያንቃት ከወንዙ ውሃ ተጎነጨለት….
“…ገና ካሁኑ አያቴ ያጣውን ተረዳሁለት" አለች ወደ ሶራ
ዙራ፡
“ድንግል ውበትን ነፃነትን እርጋታን… ነበር አያቴ ያጣው'' እንባዋ በአይኖችዋ ሞላ፡፡ “ሁካታ የሌለበት ዓለም አንዱ ሌላውን
የማይጎዳበት ተፈጥሮ ቅኝቱ የተዋሃደ ቅላፄ ነበር አያቴ ያጣው ለካ" እየሳቀች አለቀሰች፡፡ እንባዋ እየፈሰሰ ጥርሶችዋ ግን ተገለጡ
ሰዎች እውነተኛ ስሜት ሲሰማቸው ስሜታቸው ይደበላለቃል" ይህች
ፕላኔት የሚለቀስባት ካልያም የሚሳቅባት ብቻ አይደለችም፤ ደስታና
ሐዘን ሣቀና ልቅሶ እንደ ሳንቲም ገፅታ አብረው የሚኖሩባት ናት፤እና እውነተኛው የተፈጥሮ ስሜት ኮንችት ላይም ደረሰ
እንደ አያቷ ትናንትን ዛሬ ላይ ቁማ አለመችው፧ እንደ
ልጆችዋ ዛሬ ላይ ቆማ ነገን አሰበችው ተፈጥሮ እንደ ሰው አታረጅ ይሆናል እሚያቆሽሻት ሰው እስካለ ግን እንደ ትናንቱ ዛሬ
አታምርም፡ እንደ ዛሬው የውበት ፀዳሏ ለነገ አይደርስም፡፡ እና
ኮንችት ከመሃል ሆነች ከኢትዮጵያዊው አያቷና ካልወለደችው ልጅዋ መካከል!
ኮንችት የእፎይታ ትንፋሽዋን አንቦለቦለችና ሃዘንና ደስታዋን ሙሉ በሙሉ የተካ ፈገግታ ለውቡ ተፈጥሮ አበርክታ ሶራን ተመለከተችው፡፡
ኮንችት እንደ ከብቶች፥ እንደ አዕዋፍ እንደ እፅዋት ራቁቷን ብትሆን ትመረጣለች በተለይ በእንዲህ ዓይነቱ ተፈጥሮአዊ ተፈጥሮ… መመሳሰል ያረካታል።
ፓንትና ጡት ማሲያዣ ሲቀር
ሁሉንም ልብሷን አወለቀችው ልብስ ገመናን ሃፍረተ ሥጋን መሸፈኛ ነው።
እውነተኛው ተፈጥሮ ግን ገመና ሃፍረተ ስጋ የለም፡፡ ተፈጥሮ ገነት ናት አዳምና ሄዋን ዕፀ በላሷን ከመብላታቸው በፊት
እንደነበሩት።
ቤጫ መስመር በጎንና ጎኗ የተጋደመባት ሰማያዊ ቀለም ያላት የፕላስቲክ ጀልባ እየተጀነነ በኩራት ቁልቁል ይሁን ሽቅብ
መፍስሱ ግራ በሚያጋባው የኦሞ ወንዝ ላይ እንደ ቄብ ዶሮ ቂብ ብላ በአፍንጫዋ ውሃውን ግራና ቀኝ እየከፈለች ትንሳፈፋለች፡
ኮንችት አጠር ያለውንና ቢጫውን መቅዘፊያ ካስቀመጠችበት
አንስታ ከሶራ ጎን ካለው ቦታ ቁጭ ብላ በግራ እጅዋ የመቅዘፊያውን እጀታ ጨብጣ ውሃውን ሶስቴ
ገፋችና ወደ ሶራ ዞራ ፈገግ አለች፡፡ ሶራም በመቅዘፊያው ውሃውን
ወደ ኋላ እየገፋ ፈገግ አለላት፡፡
ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመችና ወደ ወንዙ ዘለለች ወደ ኦሞ ቁልቁል ሰጠመች፤ እግርና እጅዋ በስልት እየተንቀሳቀ
እንደ አሶች ውስጥ ለውስጥ ዋኘች፡፡
ሶራ መቅዘፉን አቁሞ ኮንችት ካለ ህይወት አድን ጃኬት ባዶዋን ወንዝ ውስጥ በመግባቷ ደነገጠ፡፡ ልብሱን ከመቅጽበት አውልቆ አያት ገና ብቅ አላለችም፡፡ ዘሎ ውሃው ውስጥ ገባና
በውሃው ውስጥ ለውስጥ ፈለጋት፡፡ ስማያዊዋ ጀልባ ግራ ቀኝ ተወዛወዘ ቀስ በቀስ ተረጋግታ ተንሳፈፈች፡፡ ሶራ የሆነ ድምፅ ሰማና
ሽቀብ ወደላይ ቀዘፈ:
እህ! እህ. በድካም እያቃሰተች ኮንችት ትስቃለች፡፡እሱም አብሯት ሳቀ፡ ውሃው ውስጥ ተጠጋጉ፡ ሳቀ ሳቀች ፍርስ
እያሉ ተሳሳቁ ውሃ ተራጩ የአፍሪካ ንሥር አየሩ ላይ
ይንሳፈፋል፡፡ ከዳር በኩል ውሃ ሲጠጡ የነበሩት ዝሆኖች በአድናቆት
ተመለከቷቸው
“ዝሆን የአፍሪካ ዝሆን ጆሮ ሰፊው የዝሆን ጉዞ' በሚል
በልዕልት ሚድታውን ታናል' ስርከስ ላይ ከቀረቡት ዝሆኖች ሁሉ እጅግ የገዘፈ' ብላ ኮንችት ዝሆኖችን በአድናቆት ተመሰከተቻቸው፡፡
ሶራና ኮንችት ጀልባዋ ላይ ወጡ፡፡ ሰውነታቸው በውሃ
ነጠብጣብ ተሞልቷል፡ ዝሆኖች ለምለም ጨሌ ሣር ከሚታይበት ሜዳ ወጣ አሉና አንድ ኮርማ ዝሆንና አንዲት ሴት ዝሆን መዳራት
ጀመሩ፡፡ ከጥቂት ማሽኮርመም በኋላ ወንዱ ዝሆን ያን ግዙፍ ሰውነቱን ወደ ላይ አንስቶ በኋላ እግሩ ቆመና የፊት እግሮቹን ሴቷ
ዝሆን ላይ ጭኖ የእንግሊዘኛውን ኤስ' ፊደል ቅርፅ ያለውን ብልቱን
እንደምንም ብሎ ሴቷ ብልት አስገባና ሰረራት፡፡
ኮንችትና ሶራ ያን ተፈጥሮአዊ ትርኢት አፋቸውን ከፍተው
ሲያዩ ላያቸው ላይ የነበረው የውሃ ነጠብጣብ ደረቀላቸው፡፡ የጫካው
የተፈጥሮ ድሪያ ሳባቸው፡፡ ተፈጥሮ ውስጥ የተፈጥሮ ድሪያ ያስጎመዣል ...
ኮንችት ለስላሳና ቀጥ ያሉ ጭኖችዋን አጥፋ የመቅዘፊያውን እጀታ አንስታ ለመቅዘፍ ጠምዘዝ ስትል ሰፋ ያለው ዳሌዋ ሰርጓዳው ወገቧ ጠባቡ ትከሻዋ ሰውነቷ ላይ የተለጠፈው ዞማ ፀጉሯን…
አየው! ተስገበገበ… ኮንችት እንዲህ የውበቷን ሰዲቃ ሲቋደስ ዞር ብላ ፈገግታዋን አከለችለት፡
ከወንዙ ውሃ ግራና ቀኝ ካሉት የውበት ፀዳሎች ጋር
የተጣጣመው ውበቷ እንደ ፍላፃ ሕሊናውን ወጋው፡፡ ዞር አለች እንደገና፤ ሶራ ከንፈሮቹን በቀስታ ግራና ቀኝ እንደ ላስቲክ እየለጠጠ
ዘርዘር ያሉ ጥርሶቹን አሳያት እሷም ፈገግ አለች ፈገግታዋ በመቀጣጠል ላይ ያለውን ስሜቱን ቤንዚን እንደጨመሩበት እሳት
ባንዴ ቦግ አደረገው፡፡ ሰደዱ እሷ ህሊናም በቅጽበት ደርሶ እሷንም ለበለባት…ሳይታወቃቸው እሳታቸውን ለማብረድ ሁለቱም
ከንፈሮቻቸውን በምላሳቸው አረጠቡ የአይናቸው ቆብ ቁልቁል እየወረደ ተከደነ… ዝሆኑ ሽቅብ ተነሳ. ሴቷ ተጠጋችው፡
የሚመነጭቀው እንዳለ ሁሉ ጥብቅ አድርጎ አቀፋት… ዝሆኑ!
አእዋፍ ያፏጫሉ ጀልባዋ
ትንሳፈፋለች እንቁራሪቶች
ያንቆርራሉ ኮንችት የሶራን
የእጅ ጡንቻዎች ሳም ሳም ስታደርግለት እሱ አካሏን እየላሰ ሎሚውን በእጁ ጣቶች እያሻሽ ከንፈሩና ከንፈሯ ተገናኘ ኮንችት ይበልጥ እየሰረሰረች ተጠጋችው !
ያኔ! ጎርበጥ ያለው ነገር ቆረቆራት የቆረቆራትን የቀኝ እጅዋን ሰዳ ከተደበቀበት ስታወጣው እንደ ህፃን ልጅ ፈነደቀ…
ኦሞ ወንዝ በኵራት ይፈሳል እፅዋት በንፋስ ይወዛወዛሉ
+ፈጥሮ አራዊትና አዕዋፍ ይዳራሉ:: ብርጉዱ እጣኍ ጠጅ ሳሩ ጤናዳሙ ጽጌረዳው የበረሃ እጣነ አካባቢውን አልባብ አልባብ
እሸተ† ድንቅ የተፈጥሮ ህይወት ታምር ይታያል!
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ብጠጣለት የሚጎዳኝ ይመስልሃል?"
ወራጅ ውሃ እኮ ነው። እፅዋት በልምላሜ ፈክተው ጎንበስ ቀና እያሉ የሚወዛወዙበት አራዊት እየፈነደቁ የሚፈነጥዙበት
ዋኔ ዳክዬዎች ብቅ ጥልቅ እያሉ ተጎንጭተው የሚንሳፈፉበት ወደ
ሰማዬ ሰማያት ጉነው የሚበሩበት... ውሃ የሚጎዳሽ አይመስለኝም፡፡
ስለዚህ ይህን ከብክለት ነፃ የሆነ ውሃ በእጆችሽ መዳፍ እያፈሰሽ ተጎጭው ማሬ አላት፡፡
ኮንችት እድሜዋ ባጠረ ግርምታ ተመሰከተችውና፡-
“ይገባኛል ገና አልተበከለም ገና አልቆሸሽም… ስልጣኔ
ኩሉን አልጣላበትም ቅርሻቱን አልደፋበትም… በእርግጥ ሳልፈራ መጠጣት ነበረብኝ ብላ በርከክ ብላ ሁለት እጆችዋን እንደ አካፋ አሹላ በእፍኝዋ የቀዳችውን ውሃ እንደ ወፎቹ አንጋጣ ወደ ጉሮሮዋ
አንቀረቆረችው፡ ጎርፍ መሳዩ ንፁህ ውሃ ጉሮሮዋን እያቀዘቀዛት ቁልቁል ወረደ ደስ አላት ጣማት፡፡ ስለዚህ እየደጋገመች ተጎነጨችው፡፡
ቀና ብላ አየች ሰማያዊው ሰማይ ተውቧል ! ወደ ዳርና
ዳር እፅዋትን ተመለከተች የቆላ ዋንዛ፡ ጥቁር እንጨት እንኮይ ጠዪ. ቃጫ. . . በአረንጓዴ ልምላሜ ተሞልተው ምድሯን
አስውበዋታል፡ ጉጉት ድርጭት ጂግራ ቆቅ… ወፎች ይዘምራሉ ይጯሀሉ ይስቃሉ… አቦ ሽማኔ አንበሳው ቆርኪው ዝንጀሮው ጦጣና ጉሬዛው. በእዕዋት ስር ሲርመሰመሱ፡ በእዕዋት ቅርንጫፎች
ላይ እየተንጨዋለሉ ሲወናጨፉ ይታያሉ፡፡
እባቡ እንሽላሊቱ… በዕፅዋት ግንድ
ይልወሰወሳሉ፡፡ ኦሞ ወንዝ ላይ አዞው ራሱን አውጥቶ ይንሳፈፋል፧አሶች ብቅ እያሉ ጥቡሉቅ ይላሉ….
ተፈጥሮ እንደ ሙሽራ ደምቃለች አምራለች ፈክታለች...እንደ ማራኪው የአዳም ዘመን ገነት ኑሮ! ኮንችት ያን ድንቅ ውበት
በአይኗ በጆሮዋ ባጠቃላይ በስሜት ሕዋሶችዋ እየኮረሻሽመች በላችው እንዳያንቃት ከወንዙ ውሃ ተጎነጨለት….
“…ገና ካሁኑ አያቴ ያጣውን ተረዳሁለት" አለች ወደ ሶራ
ዙራ፡
“ድንግል ውበትን ነፃነትን እርጋታን… ነበር አያቴ ያጣው'' እንባዋ በአይኖችዋ ሞላ፡፡ “ሁካታ የሌለበት ዓለም አንዱ ሌላውን
የማይጎዳበት ተፈጥሮ ቅኝቱ የተዋሃደ ቅላፄ ነበር አያቴ ያጣው ለካ" እየሳቀች አለቀሰች፡፡ እንባዋ እየፈሰሰ ጥርሶችዋ ግን ተገለጡ
ሰዎች እውነተኛ ስሜት ሲሰማቸው ስሜታቸው ይደበላለቃል" ይህች
ፕላኔት የሚለቀስባት ካልያም የሚሳቅባት ብቻ አይደለችም፤ ደስታና
ሐዘን ሣቀና ልቅሶ እንደ ሳንቲም ገፅታ አብረው የሚኖሩባት ናት፤እና እውነተኛው የተፈጥሮ ስሜት ኮንችት ላይም ደረሰ
እንደ አያቷ ትናንትን ዛሬ ላይ ቁማ አለመችው፧ እንደ
ልጆችዋ ዛሬ ላይ ቆማ ነገን አሰበችው ተፈጥሮ እንደ ሰው አታረጅ ይሆናል እሚያቆሽሻት ሰው እስካለ ግን እንደ ትናንቱ ዛሬ
አታምርም፡ እንደ ዛሬው የውበት ፀዳሏ ለነገ አይደርስም፡፡ እና
ኮንችት ከመሃል ሆነች ከኢትዮጵያዊው አያቷና ካልወለደችው ልጅዋ መካከል!
ኮንችት የእፎይታ ትንፋሽዋን አንቦለቦለችና ሃዘንና ደስታዋን ሙሉ በሙሉ የተካ ፈገግታ ለውቡ ተፈጥሮ አበርክታ ሶራን ተመለከተችው፡፡
ኮንችት እንደ ከብቶች፥ እንደ አዕዋፍ እንደ እፅዋት ራቁቷን ብትሆን ትመረጣለች በተለይ በእንዲህ ዓይነቱ ተፈጥሮአዊ ተፈጥሮ… መመሳሰል ያረካታል።
ፓንትና ጡት ማሲያዣ ሲቀር
ሁሉንም ልብሷን አወለቀችው ልብስ ገመናን ሃፍረተ ሥጋን መሸፈኛ ነው።
እውነተኛው ተፈጥሮ ግን ገመና ሃፍረተ ስጋ የለም፡፡ ተፈጥሮ ገነት ናት አዳምና ሄዋን ዕፀ በላሷን ከመብላታቸው በፊት
እንደነበሩት።
ቤጫ መስመር በጎንና ጎኗ የተጋደመባት ሰማያዊ ቀለም ያላት የፕላስቲክ ጀልባ እየተጀነነ በኩራት ቁልቁል ይሁን ሽቅብ
መፍስሱ ግራ በሚያጋባው የኦሞ ወንዝ ላይ እንደ ቄብ ዶሮ ቂብ ብላ በአፍንጫዋ ውሃውን ግራና ቀኝ እየከፈለች ትንሳፈፋለች፡
ኮንችት አጠር ያለውንና ቢጫውን መቅዘፊያ ካስቀመጠችበት
አንስታ ከሶራ ጎን ካለው ቦታ ቁጭ ብላ በግራ እጅዋ የመቅዘፊያውን እጀታ ጨብጣ ውሃውን ሶስቴ
ገፋችና ወደ ሶራ ዞራ ፈገግ አለች፡፡ ሶራም በመቅዘፊያው ውሃውን
ወደ ኋላ እየገፋ ፈገግ አለላት፡፡
ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመችና ወደ ወንዙ ዘለለች ወደ ኦሞ ቁልቁል ሰጠመች፤ እግርና እጅዋ በስልት እየተንቀሳቀ
እንደ አሶች ውስጥ ለውስጥ ዋኘች፡፡
ሶራ መቅዘፉን አቁሞ ኮንችት ካለ ህይወት አድን ጃኬት ባዶዋን ወንዝ ውስጥ በመግባቷ ደነገጠ፡፡ ልብሱን ከመቅጽበት አውልቆ አያት ገና ብቅ አላለችም፡፡ ዘሎ ውሃው ውስጥ ገባና
በውሃው ውስጥ ለውስጥ ፈለጋት፡፡ ስማያዊዋ ጀልባ ግራ ቀኝ ተወዛወዘ ቀስ በቀስ ተረጋግታ ተንሳፈፈች፡፡ ሶራ የሆነ ድምፅ ሰማና
ሽቀብ ወደላይ ቀዘፈ:
እህ! እህ. በድካም እያቃሰተች ኮንችት ትስቃለች፡፡እሱም አብሯት ሳቀ፡ ውሃው ውስጥ ተጠጋጉ፡ ሳቀ ሳቀች ፍርስ
እያሉ ተሳሳቁ ውሃ ተራጩ የአፍሪካ ንሥር አየሩ ላይ
ይንሳፈፋል፡፡ ከዳር በኩል ውሃ ሲጠጡ የነበሩት ዝሆኖች በአድናቆት
ተመለከቷቸው
“ዝሆን የአፍሪካ ዝሆን ጆሮ ሰፊው የዝሆን ጉዞ' በሚል
በልዕልት ሚድታውን ታናል' ስርከስ ላይ ከቀረቡት ዝሆኖች ሁሉ እጅግ የገዘፈ' ብላ ኮንችት ዝሆኖችን በአድናቆት ተመሰከተቻቸው፡፡
ሶራና ኮንችት ጀልባዋ ላይ ወጡ፡፡ ሰውነታቸው በውሃ
ነጠብጣብ ተሞልቷል፡ ዝሆኖች ለምለም ጨሌ ሣር ከሚታይበት ሜዳ ወጣ አሉና አንድ ኮርማ ዝሆንና አንዲት ሴት ዝሆን መዳራት
ጀመሩ፡፡ ከጥቂት ማሽኮርመም በኋላ ወንዱ ዝሆን ያን ግዙፍ ሰውነቱን ወደ ላይ አንስቶ በኋላ እግሩ ቆመና የፊት እግሮቹን ሴቷ
ዝሆን ላይ ጭኖ የእንግሊዘኛውን ኤስ' ፊደል ቅርፅ ያለውን ብልቱን
እንደምንም ብሎ ሴቷ ብልት አስገባና ሰረራት፡፡
ኮንችትና ሶራ ያን ተፈጥሮአዊ ትርኢት አፋቸውን ከፍተው
ሲያዩ ላያቸው ላይ የነበረው የውሃ ነጠብጣብ ደረቀላቸው፡፡ የጫካው
የተፈጥሮ ድሪያ ሳባቸው፡፡ ተፈጥሮ ውስጥ የተፈጥሮ ድሪያ ያስጎመዣል ...
ኮንችት ለስላሳና ቀጥ ያሉ ጭኖችዋን አጥፋ የመቅዘፊያውን እጀታ አንስታ ለመቅዘፍ ጠምዘዝ ስትል ሰፋ ያለው ዳሌዋ ሰርጓዳው ወገቧ ጠባቡ ትከሻዋ ሰውነቷ ላይ የተለጠፈው ዞማ ፀጉሯን…
አየው! ተስገበገበ… ኮንችት እንዲህ የውበቷን ሰዲቃ ሲቋደስ ዞር ብላ ፈገግታዋን አከለችለት፡
ከወንዙ ውሃ ግራና ቀኝ ካሉት የውበት ፀዳሎች ጋር
የተጣጣመው ውበቷ እንደ ፍላፃ ሕሊናውን ወጋው፡፡ ዞር አለች እንደገና፤ ሶራ ከንፈሮቹን በቀስታ ግራና ቀኝ እንደ ላስቲክ እየለጠጠ
ዘርዘር ያሉ ጥርሶቹን አሳያት እሷም ፈገግ አለች ፈገግታዋ በመቀጣጠል ላይ ያለውን ስሜቱን ቤንዚን እንደጨመሩበት እሳት
ባንዴ ቦግ አደረገው፡፡ ሰደዱ እሷ ህሊናም በቅጽበት ደርሶ እሷንም ለበለባት…ሳይታወቃቸው እሳታቸውን ለማብረድ ሁለቱም
ከንፈሮቻቸውን በምላሳቸው አረጠቡ የአይናቸው ቆብ ቁልቁል እየወረደ ተከደነ… ዝሆኑ ሽቅብ ተነሳ. ሴቷ ተጠጋችው፡
የሚመነጭቀው እንዳለ ሁሉ ጥብቅ አድርጎ አቀፋት… ዝሆኑ!
አእዋፍ ያፏጫሉ ጀልባዋ
ትንሳፈፋለች እንቁራሪቶች
ያንቆርራሉ ኮንችት የሶራን
የእጅ ጡንቻዎች ሳም ሳም ስታደርግለት እሱ አካሏን እየላሰ ሎሚውን በእጁ ጣቶች እያሻሽ ከንፈሩና ከንፈሯ ተገናኘ ኮንችት ይበልጥ እየሰረሰረች ተጠጋችው !
ያኔ! ጎርበጥ ያለው ነገር ቆረቆራት የቆረቆራትን የቀኝ እጅዋን ሰዳ ከተደበቀበት ስታወጣው እንደ ህፃን ልጅ ፈነደቀ…
ኦሞ ወንዝ በኵራት ይፈሳል እፅዋት በንፋስ ይወዛወዛሉ
+ፈጥሮ አራዊትና አዕዋፍ ይዳራሉ:: ብርጉዱ እጣኍ ጠጅ ሳሩ ጤናዳሙ ጽጌረዳው የበረሃ እጣነ አካባቢውን አልባብ አልባብ
እሸተ† ድንቅ የተፈጥሮ ህይወት ታምር ይታያል!
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
በስራ ጉዳይ ወዲህና ወዲያ ስሯሯጥ ቆይቼ ከምሽተ 3 ሰዓት ካለፈ በኃለ ነው ወደ ቤት የገባሁት፡፡ያው የተለመደ የወንደላጤ ቤቴን አየከፈትኩ ሳለ ስልኬ ተንጣረረ...በአንድ እጄ እየከፈትኩ በሌለው እጄ ከኪሴ አወጣሁና አየሁት፡፡ ልጄ ነች፡አነሳሁትና
‹‹ሄሎ የእኔ ጣፋጭ››
‹‹ያንተ ጣፋጭ አይደለሁም..ማለት እናቷ ነኝ››
‹‹ውይ እሪች ይቅርታ …ተአምር መስላኝ ነው››
‹‹አውቃለሁ..አንተ አልተሳሳትክም እኮ የደወልኩት በእሷ ስልክ ነው…አባትና ልጅ ግን የምትገርሙ ሴረኞች ናችሁ››
‹‹እንዴት ማለት››በራፉን ከፍቼ ወደውስጥ ከገባሀ በኃላ አልጋዬ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብዬ ወሬዬን ቀጠልኩ፡፡
‹‹ምን እንዴት አለው…ሁሉን ነገር ሰማሁ….በሚስጥር መገናኘትና መደዋወል ከጀመራችሁ መከራረማችሁን….አረ ጭካኔያችሁ…. ከአንተ ደግሞ የእሷ አይገረምም፡፡››
‹‹እንዴት?››
‹‹ሰው እንዴት ከገዛ እናቱና አያቱ እንዲህ አይነት ሚስጥር ሰውሮ መቆየት ይችላል….ለዛውም በዚህ እድሜዋ››
‹‹ያው የአባት ጉዳይ ሲሆን ይችላል.ልጄን ደግሞ ታውቂያታለሽ… ልክ እንደአባቷ እስማርት ነች፡፡››
‹‹ይሀቺ ጉራ አሁንም አለቀቀችህም››
‹‹ምነው ተሳሳትኩ አንዴ?››
‹‹አላልኩም….ለማንኛውም በጣም እንዳስደመማችሁኝም እንዳስቀናችሁኝም መናገር እፈልጋለሁ…ለመሆኑ አንተስ እንዴት ነህ…?››
‹‹ይመስገነው… ህይወት እንደጢባ ጢቢ አንቀርቅባ አንቀርቀባ ገና አሁን በቅርብ ቀን ነው እያረጋጋቺኝ ያለው››
‹‹በጣም አዝናለሁ››
‹‹ለምኑ?››
‹‹ከእኔ ጋር የሆነው ነገር ባይሆን ኖሮ አንተ አንዱንም ችግር አታይም ነበር…››
‹‹ተይ ተይ ..ችግሩር ያየሁት እኮ ሀገሪቱ ተምሬ በተመረቅኩት ሞያ ስራ ልትሰጠኝ ስላልቻለች ነው››
‹‹ያ እውነት እንዳልሆነ ሁለታችንም እናውቃለን››
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹አንተ ስራ አጣሁ የሚለውን እንደሽፋን ተጠቅመህ እራስህን እየቀጣህ ነበር...ቤተሰቦቼ ላይ ከሰራሁት መጥፎ ስራ አንፃር የተሻለ ህይወት ፈፅሞ አይገባኝም ብለህ በመወሰን ነው በዝቅተኛ ህይወት ውስጥ እራስህን ዘፍቀህ በችግር በመዳከር እራስህን ስትቀጣ የኖረከው…እንጂ ሌላውን ተው አዲስአባ ወላጆችህ ትተውልህ የሞቱት ቤት እንዳለ ታውቃለህ….ባንክ ውስጥም ቢያንስ ከግማሽሚሊዬን ብር በላይ ትተው መሞታቸውን ከቤት ኪራይ እየተሰበሰበ ለዘመናት የተጠራቀመው ብር እንዳለ ታውቃለህ… ይሄ ሁሉ ሀብት ያለው ሰው በጤናው የፓርኪንግ ሰራተኝነት እና የሆቴል አስተናጋጅ ሆኖ የወጣትነት ህይወቱን አይገፋም…ለዛውም ባለዲግሪ ሆኖ..
‹‹ትክክል ልትሆኚ ትቺያለሽ…..እኔ ግን በዚህ መንገድ አይቼው አላውቅም…እኔ ያምትይውን ብር ሆነ ቤት መጠቀም ያልቸልኩት ሳልፈልግ ቀርቼ ሳይሆን እሱን ለመጠቀም የእቴቴን አይን ማየት ስላልፈለኩ ነው፡፡››
‹‹ተው ተው..ትንሽ ካሰብክበት እኮ የእቴቴን አይን ሳታይ የሚገባህን ንብረትህን እጅህ ማስገባት ትችል ነገር››
‹‹ተይ ተይ .እንደምታስቢው ቀላል አልነበረም››
‹‹አውቃለሁ… ግን ያደረከው ያልኩትን ነው እራስህን መቅጣት.እኔም አኮ ስላደረኩት ነው እንደዛ የምልህ…..?››
‹‹እንዴት?››
‹‹ያው እደምታየኝ አምሮብኛል ሰውነቴ አብረቀርቆል..ግን አሜሪካ ያሳለፍኳቸውን ስድስት አመቶች እንደምታስበው እንዳይመስልህ.. ከጥዋት እስከ ሊሊት ከሶስት በላይ ስራ እሰራለሁ..ብዙ ብዙ ገንዘብ አገኛለሁ..የማያስፈልገኝን ገንዘብ ለማግኘት ማለት ነው እንደዛ እለፋ የነበረው.. ማንንም አላገኝም ..የትም ሄጄ መዝናናት አልፈልግም….የሳምንት እረፍቴ ከስድስት ሰዓት አይበልጥም ነበር…ማን መሆኔን እራሱ ዘንግቼ በድኔ ልክ እንደሮቦት ሆኜ ነበር የምንቀሳቀሰው…አሁን በቅርብ ጊዜ ግን ይህ ጉዳይ እንዴት ነው..?ለምድነው እንደዚህ የምለፋው..?የምሰበስበው ገንዘብ ለማን ብዬ ነው….?ብዬ ሳስብ በጣም ግራ ተጋባሁ እና ባለሞያ ጋር ሄድኩ.. ባለሞያውም የህይወት ታሪኬን ካስለፈለፉኝ በኃላ በስተመጨረሻ የደረሰበት መደምደሚያ የምሰራው ስራ ሁሉ እራስን መቅጣት እንደሆነ እና ከዚህ ወጥመድ የመውጫው መንገድ ግን ይሄ እንዳልሆነ መከረኝ….ለዛ ነው ካለእቅዴ ድንገት ወደሀገሬ ፈጥኜ የመጣሁት..መድሀኒቱ እዚህ ስለሆነ…››
‹‹አልገባኝም›አልኳት
የእውነትም ስላልገባኝ፡፡
‹‹አየህ ያባለሞሞው ውሳኔዬ በጣም ትክክል ነበረ..ይሄው ወደ ሀገሬ ከተመለስኩ በኃላ ካስብኩት በጣም በፈጠነ ጊዜ መድሀኒቱን አግኝቼ እየታከምኩ ነው…አንተን ማግኘትና ያለህበትን ሁኔታ መረዳት ችያለሁ….ይህ ማለት በእየለቱ የት ወድቆ ይሆን በሚል እምሮዬን ሲበላኝ የነበረው ነገር አሁን ድኖልኛል….ሌላው የእቴቴን ይቅርታ ማግኘት ችያለሁ…ያ ደግሞ ምን ያህል የአእምሮ ሰላም እንደሚሰጥ በራስህ ታውቀዋለህ…በነገራችን ላይ አባዬንም ይቅርታ ጠይቄዋለሁ.. አሁን የቀረኝ ትንሽ ነገር ነው…አንተን እና አባዬን ማገናኘት..››
‹‹አንተን እና አባዬን…?››ደንግጬ
‹‹አዎ ምነው ያንን ማድረግ አትፈልግም እንዴ?››
‹‹አረ በጣም ፈልጋለሁ..ግን እንዴት ብዬ አይኑን አያለሁ ?››
‹‹ልክ የማዬን አይን እንዳየህ..ደግሞ እኔ አፍጥጬ ሄጄ እሱን ማናገር ከቻልኩ አንተስ እንዴት ያቅትሀል?፡፡:ከዛ ከእማዬ ጋር መልሰን እናጋባቸዋለን…አንድ ላይ ሆነን ወላጀቻችንን ሆነ እህቶቻችንን አንክሳቸዋለን… በእኛ ምክንያት የቆሰለው ልባቸው ፈፅሞ እንዲድን የተቻለንን እናደርጋለን..ከዛ የእኛም ቁስል ቀስ እያለ ሙሉ በሙሉ ይድናል…ምን ይታወቃል የፈረሰ ተስፋችን መልሶ ይገነባ ይሆናል…እርግጠኛ ነኝ በመጨረሻ እራሳችንንም ይቅር እንላለን፡፡
‹‹አሜሪካ ተመልሰሽ እትሄጂም ማለት ነው?››
‹‹ሄዳለሁ.. ግን ለመኖር አይደለም…ሁኔታዎችን አመቻችቼ አንደኛዬን ጠቅልዬ እመጣለሁ..››
‹‹የእውነትሽን ነው?››
‹‹ምነው ደነገጥክ…እዛ ብኖር ይሻላል እንዴ?››
‹‹አረ እንደዛ ስለወሰንሽ በጣም ደስተኛ ነኝ››
‹‹በጣም ደስተኛ ለምን እንደሆንክ ማወቅ እችላለሁ?››
‹‹እንዴ ትቀልጂያለሽ እንዴ…አንድ ቀን ታአምርን ወደአሜሪካ ልውሰድሽ ብትላት ምንድነው የማደርገው? በሚል ስጋት እንዴት እየተሰቃየሁ እንደነበር ግምቱ የለሽም››
‹‹ይገርማል?››
‹‹ምኑ?››
‹‹መልስህ ያልገመትኩት ነው..ለልጅህ ባለህ ፍቅር ቅናት አደረብኝ››
‹‹እሷ እኮ የከሰመ ህይወቴን መልሳ ያለመለመችልኝ ካሳዬ ነች. .ለእሷ ስል ህይወቴን እሰጣለሁ..››
‹‹በነገራችን ላይ አዲስአበባ ሪል እስቴት ገዝቼያለሁ..ስለዚህ ልክ ጉዳዬን ጨርሼ ከአሜሪካ እንደተመለስኩ ሁለችንም አንድ ላይ እንኖራለን ማለት ነው..››
‹‹አንድ ላይ ስትይ….?ማለት….?እንዴት…?››
የፈራሁት ነገር ዞሮ ሊመጣ ነው ብዬ በማሰብ ተርበበተበትኩ.
‹‹አይዞህ አትደንግጥ…ይሄውልህ እዬቤ እኔ አሁንም በጣም አፈቅርሀለሁ…እሱን ስሜቴን ካንተም ሆነ ከማንም መደበቅ አልችልም፡፡ደግሞም .አንተን ማፍቀር መቼም አላቆምም…ግን ደግሞ ከዚህ በፊት የሰራነውን ስህተት መቼም ደግመን እንድንሰራ አልፈልግምም፤ አልፈቅድምም….፡፡ይሄንን ደግሞ በቀደም እማዬ ሁለት ጡቶቾን እስይዛ
ነው ያስማለችኝ..ስለማልኩ ብቻ ሳይሆን የመጀመሪያውም ስህታችን ያስከፈለንን መከራ አይቼ ዳግመኛ ተመሳሳዩን ስህተት ለመፈፀም ጥንካሬው የለኝም፡፡.ቢያንስ ለእናቴ ስል….ለእህቶቼ ስል..ለአንተ ስል…፡፡ስለዚህ ምንም ስጋት አይግባህ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
በስራ ጉዳይ ወዲህና ወዲያ ስሯሯጥ ቆይቼ ከምሽተ 3 ሰዓት ካለፈ በኃለ ነው ወደ ቤት የገባሁት፡፡ያው የተለመደ የወንደላጤ ቤቴን አየከፈትኩ ሳለ ስልኬ ተንጣረረ...በአንድ እጄ እየከፈትኩ በሌለው እጄ ከኪሴ አወጣሁና አየሁት፡፡ ልጄ ነች፡አነሳሁትና
‹‹ሄሎ የእኔ ጣፋጭ››
‹‹ያንተ ጣፋጭ አይደለሁም..ማለት እናቷ ነኝ››
‹‹ውይ እሪች ይቅርታ …ተአምር መስላኝ ነው››
‹‹አውቃለሁ..አንተ አልተሳሳትክም እኮ የደወልኩት በእሷ ስልክ ነው…አባትና ልጅ ግን የምትገርሙ ሴረኞች ናችሁ››
‹‹እንዴት ማለት››በራፉን ከፍቼ ወደውስጥ ከገባሀ በኃላ አልጋዬ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብዬ ወሬዬን ቀጠልኩ፡፡
‹‹ምን እንዴት አለው…ሁሉን ነገር ሰማሁ….በሚስጥር መገናኘትና መደዋወል ከጀመራችሁ መከራረማችሁን….አረ ጭካኔያችሁ…. ከአንተ ደግሞ የእሷ አይገረምም፡፡››
‹‹እንዴት?››
‹‹ሰው እንዴት ከገዛ እናቱና አያቱ እንዲህ አይነት ሚስጥር ሰውሮ መቆየት ይችላል….ለዛውም በዚህ እድሜዋ››
‹‹ያው የአባት ጉዳይ ሲሆን ይችላል.ልጄን ደግሞ ታውቂያታለሽ… ልክ እንደአባቷ እስማርት ነች፡፡››
‹‹ይሀቺ ጉራ አሁንም አለቀቀችህም››
‹‹ምነው ተሳሳትኩ አንዴ?››
‹‹አላልኩም….ለማንኛውም በጣም እንዳስደመማችሁኝም እንዳስቀናችሁኝም መናገር እፈልጋለሁ…ለመሆኑ አንተስ እንዴት ነህ…?››
‹‹ይመስገነው… ህይወት እንደጢባ ጢቢ አንቀርቅባ አንቀርቀባ ገና አሁን በቅርብ ቀን ነው እያረጋጋቺኝ ያለው››
‹‹በጣም አዝናለሁ››
‹‹ለምኑ?››
‹‹ከእኔ ጋር የሆነው ነገር ባይሆን ኖሮ አንተ አንዱንም ችግር አታይም ነበር…››
‹‹ተይ ተይ ..ችግሩር ያየሁት እኮ ሀገሪቱ ተምሬ በተመረቅኩት ሞያ ስራ ልትሰጠኝ ስላልቻለች ነው››
‹‹ያ እውነት እንዳልሆነ ሁለታችንም እናውቃለን››
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹አንተ ስራ አጣሁ የሚለውን እንደሽፋን ተጠቅመህ እራስህን እየቀጣህ ነበር...ቤተሰቦቼ ላይ ከሰራሁት መጥፎ ስራ አንፃር የተሻለ ህይወት ፈፅሞ አይገባኝም ብለህ በመወሰን ነው በዝቅተኛ ህይወት ውስጥ እራስህን ዘፍቀህ በችግር በመዳከር እራስህን ስትቀጣ የኖረከው…እንጂ ሌላውን ተው አዲስአባ ወላጆችህ ትተውልህ የሞቱት ቤት እንዳለ ታውቃለህ….ባንክ ውስጥም ቢያንስ ከግማሽሚሊዬን ብር በላይ ትተው መሞታቸውን ከቤት ኪራይ እየተሰበሰበ ለዘመናት የተጠራቀመው ብር እንዳለ ታውቃለህ… ይሄ ሁሉ ሀብት ያለው ሰው በጤናው የፓርኪንግ ሰራተኝነት እና የሆቴል አስተናጋጅ ሆኖ የወጣትነት ህይወቱን አይገፋም…ለዛውም ባለዲግሪ ሆኖ..
‹‹ትክክል ልትሆኚ ትቺያለሽ…..እኔ ግን በዚህ መንገድ አይቼው አላውቅም…እኔ ያምትይውን ብር ሆነ ቤት መጠቀም ያልቸልኩት ሳልፈልግ ቀርቼ ሳይሆን እሱን ለመጠቀም የእቴቴን አይን ማየት ስላልፈለኩ ነው፡፡››
‹‹ተው ተው..ትንሽ ካሰብክበት እኮ የእቴቴን አይን ሳታይ የሚገባህን ንብረትህን እጅህ ማስገባት ትችል ነገር››
‹‹ተይ ተይ .እንደምታስቢው ቀላል አልነበረም››
‹‹አውቃለሁ… ግን ያደረከው ያልኩትን ነው እራስህን መቅጣት.እኔም አኮ ስላደረኩት ነው እንደዛ የምልህ…..?››
‹‹እንዴት?››
‹‹ያው እደምታየኝ አምሮብኛል ሰውነቴ አብረቀርቆል..ግን አሜሪካ ያሳለፍኳቸውን ስድስት አመቶች እንደምታስበው እንዳይመስልህ.. ከጥዋት እስከ ሊሊት ከሶስት በላይ ስራ እሰራለሁ..ብዙ ብዙ ገንዘብ አገኛለሁ..የማያስፈልገኝን ገንዘብ ለማግኘት ማለት ነው እንደዛ እለፋ የነበረው.. ማንንም አላገኝም ..የትም ሄጄ መዝናናት አልፈልግም….የሳምንት እረፍቴ ከስድስት ሰዓት አይበልጥም ነበር…ማን መሆኔን እራሱ ዘንግቼ በድኔ ልክ እንደሮቦት ሆኜ ነበር የምንቀሳቀሰው…አሁን በቅርብ ጊዜ ግን ይህ ጉዳይ እንዴት ነው..?ለምድነው እንደዚህ የምለፋው..?የምሰበስበው ገንዘብ ለማን ብዬ ነው….?ብዬ ሳስብ በጣም ግራ ተጋባሁ እና ባለሞያ ጋር ሄድኩ.. ባለሞያውም የህይወት ታሪኬን ካስለፈለፉኝ በኃላ በስተመጨረሻ የደረሰበት መደምደሚያ የምሰራው ስራ ሁሉ እራስን መቅጣት እንደሆነ እና ከዚህ ወጥመድ የመውጫው መንገድ ግን ይሄ እንዳልሆነ መከረኝ….ለዛ ነው ካለእቅዴ ድንገት ወደሀገሬ ፈጥኜ የመጣሁት..መድሀኒቱ እዚህ ስለሆነ…››
‹‹አልገባኝም›አልኳት
የእውነትም ስላልገባኝ፡፡
‹‹አየህ ያባለሞሞው ውሳኔዬ በጣም ትክክል ነበረ..ይሄው ወደ ሀገሬ ከተመለስኩ በኃላ ካስብኩት በጣም በፈጠነ ጊዜ መድሀኒቱን አግኝቼ እየታከምኩ ነው…አንተን ማግኘትና ያለህበትን ሁኔታ መረዳት ችያለሁ….ይህ ማለት በእየለቱ የት ወድቆ ይሆን በሚል እምሮዬን ሲበላኝ የነበረው ነገር አሁን ድኖልኛል….ሌላው የእቴቴን ይቅርታ ማግኘት ችያለሁ…ያ ደግሞ ምን ያህል የአእምሮ ሰላም እንደሚሰጥ በራስህ ታውቀዋለህ…በነገራችን ላይ አባዬንም ይቅርታ ጠይቄዋለሁ.. አሁን የቀረኝ ትንሽ ነገር ነው…አንተን እና አባዬን ማገናኘት..››
‹‹አንተን እና አባዬን…?››ደንግጬ
‹‹አዎ ምነው ያንን ማድረግ አትፈልግም እንዴ?››
‹‹አረ በጣም ፈልጋለሁ..ግን እንዴት ብዬ አይኑን አያለሁ ?››
‹‹ልክ የማዬን አይን እንዳየህ..ደግሞ እኔ አፍጥጬ ሄጄ እሱን ማናገር ከቻልኩ አንተስ እንዴት ያቅትሀል?፡፡:ከዛ ከእማዬ ጋር መልሰን እናጋባቸዋለን…አንድ ላይ ሆነን ወላጀቻችንን ሆነ እህቶቻችንን አንክሳቸዋለን… በእኛ ምክንያት የቆሰለው ልባቸው ፈፅሞ እንዲድን የተቻለንን እናደርጋለን..ከዛ የእኛም ቁስል ቀስ እያለ ሙሉ በሙሉ ይድናል…ምን ይታወቃል የፈረሰ ተስፋችን መልሶ ይገነባ ይሆናል…እርግጠኛ ነኝ በመጨረሻ እራሳችንንም ይቅር እንላለን፡፡
‹‹አሜሪካ ተመልሰሽ እትሄጂም ማለት ነው?››
‹‹ሄዳለሁ.. ግን ለመኖር አይደለም…ሁኔታዎችን አመቻችቼ አንደኛዬን ጠቅልዬ እመጣለሁ..››
‹‹የእውነትሽን ነው?››
‹‹ምነው ደነገጥክ…እዛ ብኖር ይሻላል እንዴ?››
‹‹አረ እንደዛ ስለወሰንሽ በጣም ደስተኛ ነኝ››
‹‹በጣም ደስተኛ ለምን እንደሆንክ ማወቅ እችላለሁ?››
‹‹እንዴ ትቀልጂያለሽ እንዴ…አንድ ቀን ታአምርን ወደአሜሪካ ልውሰድሽ ብትላት ምንድነው የማደርገው? በሚል ስጋት እንዴት እየተሰቃየሁ እንደነበር ግምቱ የለሽም››
‹‹ይገርማል?››
‹‹ምኑ?››
‹‹መልስህ ያልገመትኩት ነው..ለልጅህ ባለህ ፍቅር ቅናት አደረብኝ››
‹‹እሷ እኮ የከሰመ ህይወቴን መልሳ ያለመለመችልኝ ካሳዬ ነች. .ለእሷ ስል ህይወቴን እሰጣለሁ..››
‹‹በነገራችን ላይ አዲስአበባ ሪል እስቴት ገዝቼያለሁ..ስለዚህ ልክ ጉዳዬን ጨርሼ ከአሜሪካ እንደተመለስኩ ሁለችንም አንድ ላይ እንኖራለን ማለት ነው..››
‹‹አንድ ላይ ስትይ….?ማለት….?እንዴት…?››
የፈራሁት ነገር ዞሮ ሊመጣ ነው ብዬ በማሰብ ተርበበተበትኩ.
‹‹አይዞህ አትደንግጥ…ይሄውልህ እዬቤ እኔ አሁንም በጣም አፈቅርሀለሁ…እሱን ስሜቴን ካንተም ሆነ ከማንም መደበቅ አልችልም፡፡ደግሞም .አንተን ማፍቀር መቼም አላቆምም…ግን ደግሞ ከዚህ በፊት የሰራነውን ስህተት መቼም ደግመን እንድንሰራ አልፈልግምም፤ አልፈቅድምም….፡፡ይሄንን ደግሞ በቀደም እማዬ ሁለት ጡቶቾን እስይዛ
ነው ያስማለችኝ..ስለማልኩ ብቻ ሳይሆን የመጀመሪያውም ስህታችን ያስከፈለንን መከራ አይቼ ዳግመኛ ተመሳሳዩን ስህተት ለመፈፀም ጥንካሬው የለኝም፡፡.ቢያንስ ለእናቴ ስል….ለእህቶቼ ስል..ለአንተ ስል…፡፡ስለዚህ ምንም ስጋት አይግባህ
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
"ሰጥሀለው መጀመሪያ ልብስህን አውልቅ ..፡፡››አለችና ጎንበስ ብላ ጫማዋን አወለቀችለት ..ከዛ የሱሪውን ቀበቶ ፈታችና ቁልፍን ከፍተች… ዚፑን ወደታች በማንሸራተት ሁለቱን እግሮቹን ከታች በመያዝ እንደምንም እየጎተተች ከላይ እየሳበች ሱሪውን ከፓንቱ ጋር አንድ ላይ ሞሽልቃ አወለቀች…..እንዲህ ጨርቅ ሆኖ እንትኑ አደባባይ መሀል የቆመ የነፃነት ሀውልት ይመስላል....‹‹ልዩ ይሄን የመሰለ ዕቃ ለሌላ አሳልፈሽ ከመስጠትሽ በፊት አንዴ ብትጠቀሚው?››የሚል ሴጣናዊ ምክር የሆነ መንፈስ በጆሮዬ ሹክ አለባት። ጆሮዋን ደፈነችና ተልዕኮዋን ላይ አተኮረች...አሁን የቀረው ፓካውቱን ማውለቅ ነው ሙሉ በሙሉ አልጋው ላይ ወጣችና እንደምንም ታግላ አወለቅችለት.. አሁን ሙሉ እርቃኑን ቀርቷል..አልጋ ላይ ቆማ ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ በትኩረት አይኖቾን እያመላለስች አየችው፡፡ ወንድ ልጅን እንዲህ መለመላውን በአካል ስታይ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው። ጥሩ የተባለ የእስፓርተኛ ሰውነት ከተመጠነ ውፍረትና ቁመት ጋር ነው ያለው ..እንዲያም ሆኖ ግን የወንድ አካላዊ ቁመና እንደሴት ማራኪ አይደለም ስትል አብሰለሰለች። ‹‹አሁን ይሄን ማሰቢ ጊዜ ነው ?››እራሷን ገሰፅችና ወደሳሎን ተመለሰች...ጊፍቲ አሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ እጅ አልሰጠችም" አሁንም የመጠጥ ብርጮቆዋን በእጇ እንደያዘች... እያላዘነች ነው፡፡
"ቃልዬ አሁን ናልኝ...ናና ሰውነቴን ዳብሰው...ናና ከንፈሬን ምጠጠው...ናና ጡቶቼን ጭመቃቸው...ናና ጭኖቼን ገነጣጥላቸው...ናና ..››
‹‹..ቃልዬን ፈልገሽው ነው?"
"አዎ ...ቃልዬን አምጪልኝ "
"ቃልዬን እንዳመጣልሽ...መጀመሪያ የያዝሽውን መጠጥ ጠጪ"
"መጠጥ ይሄው"
በአንድ ትንፋሽ ግልብጥ አደረገችው" ይሄው ጨረስኩ በያ አምጪልኝ"
"አመጣዋለሁ ..ግን ከአመጣሁት ትሰጪዎለሽ"
"ለቃልዬ..በደንብ ነዋ ...ለዛውም እንደፈለገው፡፡"
"እንቢ አልፈልግም ካለስ?"
"አንቺ ብቻ አምጪልኝ እንጂ በግድ ነው የምሰጠው..?"
‹‹እንግዲህ ተነሽ...ቃልዬ ልብሱን አወላልቆ ዝግጅ ሆኖ እየጠበቀሽ ነው...››
የእውነት ፈጥና መቀመጫዋን ለቃ ለመነሳት ብትሞክርም መቀመጫዋን ከሶፍው መላቀቅ አልቻለችም...ክንዷን ይዛ በመጎተት አስነሳቻትና እየጎተተች ማለት ይቻላል..ወደራሳቸው መኝታ ቤት ይዛት ገባች... መድህኔን ጠቅልላ እንዳስተኛችው ተኝቷል።
"የተኛ ሰው በማየቷ "ቃልዬ ነው እንዴ?"ስትል በተኮለታተፈ እና በተሰባበረ አረፍተ ነገር ጠየቀች፡፡
‹‹አዎ ግን በመስከርሽ እንዳይበሳጭ ድምፅሽን ቀንሺ አለቻት...በሁለት እጇ አፏን ፡አፈነች...አልጋው ጫፍ አስቀመጥኳት ‹‹...አሁን ልብስሽን ላውልቅልሽ..ተስማማሽ?›› ልክ እንደ መድህኔ እንዳደረገችው እያንዳንድን በሰውነቷ ላይ ያለውን ልብስ አወለቀችላትና መለመላዋን አስቀረቻት‹‹...ፐ ቅርፅ...›› በሚል አድናቆት እየጎተተች ከውስጥ አስገባቻት …እና ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብላ ‹‹እንግዲህ እኔ ሄድኩልሽ ..ያው ቃልዬ በደንብ ስጪው" አለቻት፡፡፡
መዲህኔ ላይ እየተጣበቀችበት‹‹ እ…ሺ ››.አለችን
መብራቱን አጠፍችና ከአልጋው ወረደች ..ተራመደችና ከክፍሉ አልወጣችም፤ እዛው መግቢያ ላይ ወዳለ ሶፍ ሄደችና ጋደም አለች...ከዛ የሚፈጠረውን ነገር መከታተል ጀመረች...
"ቃል አንተ ተኛህ እንዴ...?››ጊፍቲ ነች መድሀኔን እየወዘወዘች ያለችው፡፡
"አለው ....ልዪዬ"በሰመመን ውስጥ ሆኗ መለሰላት፡፡
"ከዛ የመተሻሸት ድምፅ ተሰማ ..ልዩ የሞባይሏን መብራት አበራችና ወደእነሱ አተኮረች ..ጊፍቲ እላዪ ላይ ወጥታበት ጎንበስ ብላ ከንፈሩን እየላሰችው ነው...ወገቧን ጨምቆ ይዞታል‹‹...ከደቂቃዎች በፊት ሁለቱም ተዝለፍልፈው እሬሳ መስለው አልነበረ እንዴ?›› ስትል በመገረም በውስጧ ጠየቀች፡፡ እንዲህ ልትል የቻለችው አንደኛው አንደኛውን ሲጨምቅና አንደኛው አንደኛውን በጥንካሬ ሲያንከባልል በማየቷ ነው....ከላይ አልብሳቸው የነበረ አልጋ ልብስም ሆነ ብርድ ልብስ ከላያቸው ተንሸራቶ ወደመሬት ወደቀ...አሁን ሁሉ ነገር በግልፅ ይታያት ጀመር...ሲተሻሹ..ሲሳሳሙ እና ሲዋሰብ በቂ የሆነ ፎቶም ቪዲዬም ቀረፀቻቸው፡፡.
ከዛ እነሱ እስኪረኩ መታገስ ከብዷት መሬት ካዝረከረኩት ልብስ ብድርብሱን ትታላቸው አልጋልብሱን ወሰደችና እሱን ተከናንባ እዛው ሶፋ ላይ ተኝች‹‹..እስቲ ሌሎች ሶስት መኝታ ክፍሎች ነበሩ ለምን እዛ ሄጄ አልተኛሁም..?››ስትል ጠየቀች…ምክንያቱን ግን አታውቀውም ነበር፡፡ወዲያው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት… ከእንቅልፏ ባና ሰዓቷን ሳታይ 12.10 ሆኖ ነበር..አይኗን አሻሽታ አልጋውን ስትመለከት ማመን አልቻለችም… ጊፍቲ መድሀኔ ክንድ ላይ ተንተርሳ አንደኛውን እግሩን ጭኖቾ መካከል ሰንቅሮ አንደኛውን ደግሞ ከላዬ ጭኖባት ጭልጥ ያለ እንቀለፍ ውስጥ ገብተው ያንኮራፋሉ… ማንኮራፋታቸው እራሱ ተራ በተራ ስለሆነ የራሱ የሆነ ስልተ ምት አለው….ከሶፋዋ ተነሳችና ቆመች.. .መኝታው ሰላልተመቻት ሰውነቷ ድቅቅ ብሏል…ተራመደች…ወደአልጋው ተጠጋችና እሪ ብላ ጩኸቷን ለቀቀችው……በመበርግ ሁለቱም ከእንቅልፋቸው ባነኑና ከተጣበቁበት ተላቀቁ፤ አንዴ እሷን አንዴ እርስ በረስ መተያየት ጀመሩ…፡፡
እሷ እንደድንቅ ብሄራዊ ተያትር ቤት ተዋናዬች ባጠናችውና በተዘጋጀችው መሰረት መድረኩን ተቆጠጣጠረችው፡
‹‹እንዴት እንዲህ ታደርጉኛላችሁ…ሰክራለች ብላችሁ እኔን ሶፋላ ላይ አስተኝታችሁ…?መድሀኒ ይሄ ለእኔ ይገባል.?››እራሷን ነጨች..ኸረ እንባዋ ሁሉ እየረገፈ ነው..መድሀኔ ተነስቶ ከአልጋው ወረደ… መለመላውን ሁለት ሴቶች ፊት ተገተረ….ጊፍቲ አንሶላውን ሰበሰበችና እርቃኖን ሸፈነች…ፊቷ በእፍረትና ግራ በመጋባት በአንዴ ሲገረጣ እየታየ ነው..
‹‹ልዩ ተረጋጊ …ምን እንደተፈጠረ በእውነት አላውቅም..››ወላል ላይ የተበታተነውን ልብሱን መሰብሰብ ጀመረ…ከመሀከል ፓንቱን እነሳና ለበሰ..፡፡
‹‹ሁለታችሁንም ከዛሬ ጀምሮ በአይኔ ማየት አልፈልግም….ያው ከመሀከላችሁ ወጥቼለሁ....እቤቱንም ተጋብታችሁ ልትኖሩበት ትችላላችሁ፡፡››
‹‹አረ ልዩ እንደዛ አይደለም…ይሄ ስህተት ነው››ጊፍቲ ነች እራሷን እንደምንም አበረታታ መናገር የጀመረችው፡፡
‹‹ምንም ስህተት አይደለም...እንደውም አሁን ሳስበው ይሄ ጉዳይ ከእኔም ሆነ ከቃል ጀርባ ሆናችሁ ስትፈፅሙት ዛሬ የመጀመሪያችሁ አይመስለኝም.››ነገሩን አንቦረቀቀችው፡፡
እንደ እብድ እየተወራጨችና እየተራገመች መኝታ ቤቱን ለቃ ወጣች፡፡ ሊለብስ ያዘጋጀውን ሱሪ በእጁ እንዳንከረፈፈ ሊከተላት ሞከረ….አልሰማችውም፡፡ ተንደርድራ ግቢውን ለቃ ወጣችና .ወዲያው ታክሲ ውስጥ ገባችና ከአካባቢው ተሰወረች…ስልኳን አጠፋችው፡፡
ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው…..እናቷን እንኳን በቅጡ ሰላም ሳትል ወደ ክፍሏ ገባችና ከውስጥ ቀርቅሬ አልጋዋ ላይ ወጣች፡፡ድንግርግር ያለ ስሜት ነው እየተሰማት ያለው፡፡ ያሰበችውን ያህል ደስታ አልተሰማትም…ግን ቢሆንም ያሰበችውን በእቅዷ መሰረት ፈፅማዋለች....አሁን የሚቀራት ስህተቱን ተከትሎ መድህኔና ጊፊቲ ግንኙነታቸውን በዛው እንዲቀጥሉ ማድረግ ሲሆን በቀጣይነት ደግሞ ብቻውን የሚቀረውን ቃልን ብቻዋን ወደአለችው ወደራሷ ማምጣት…አዎ የመጨረሻ ግቧ ያ ነው፡፡አሁን መተኛት ስለፈለገች በአልጋ ልብሱ ሙሉ አካሏን ሸፈነች፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
"ሰጥሀለው መጀመሪያ ልብስህን አውልቅ ..፡፡››አለችና ጎንበስ ብላ ጫማዋን አወለቀችለት ..ከዛ የሱሪውን ቀበቶ ፈታችና ቁልፍን ከፍተች… ዚፑን ወደታች በማንሸራተት ሁለቱን እግሮቹን ከታች በመያዝ እንደምንም እየጎተተች ከላይ እየሳበች ሱሪውን ከፓንቱ ጋር አንድ ላይ ሞሽልቃ አወለቀች…..እንዲህ ጨርቅ ሆኖ እንትኑ አደባባይ መሀል የቆመ የነፃነት ሀውልት ይመስላል....‹‹ልዩ ይሄን የመሰለ ዕቃ ለሌላ አሳልፈሽ ከመስጠትሽ በፊት አንዴ ብትጠቀሚው?››የሚል ሴጣናዊ ምክር የሆነ መንፈስ በጆሮዬ ሹክ አለባት። ጆሮዋን ደፈነችና ተልዕኮዋን ላይ አተኮረች...አሁን የቀረው ፓካውቱን ማውለቅ ነው ሙሉ በሙሉ አልጋው ላይ ወጣችና እንደምንም ታግላ አወለቅችለት.. አሁን ሙሉ እርቃኑን ቀርቷል..አልጋ ላይ ቆማ ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ በትኩረት አይኖቾን እያመላለስች አየችው፡፡ ወንድ ልጅን እንዲህ መለመላውን በአካል ስታይ የመጀመሪያ ጊዜዋ ነው። ጥሩ የተባለ የእስፓርተኛ ሰውነት ከተመጠነ ውፍረትና ቁመት ጋር ነው ያለው ..እንዲያም ሆኖ ግን የወንድ አካላዊ ቁመና እንደሴት ማራኪ አይደለም ስትል አብሰለሰለች። ‹‹አሁን ይሄን ማሰቢ ጊዜ ነው ?››እራሷን ገሰፅችና ወደሳሎን ተመለሰች...ጊፍቲ አሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ እጅ አልሰጠችም" አሁንም የመጠጥ ብርጮቆዋን በእጇ እንደያዘች... እያላዘነች ነው፡፡
"ቃልዬ አሁን ናልኝ...ናና ሰውነቴን ዳብሰው...ናና ከንፈሬን ምጠጠው...ናና ጡቶቼን ጭመቃቸው...ናና ጭኖቼን ገነጣጥላቸው...ናና ..››
‹‹..ቃልዬን ፈልገሽው ነው?"
"አዎ ...ቃልዬን አምጪልኝ "
"ቃልዬን እንዳመጣልሽ...መጀመሪያ የያዝሽውን መጠጥ ጠጪ"
"መጠጥ ይሄው"
በአንድ ትንፋሽ ግልብጥ አደረገችው" ይሄው ጨረስኩ በያ አምጪልኝ"
"አመጣዋለሁ ..ግን ከአመጣሁት ትሰጪዎለሽ"
"ለቃልዬ..በደንብ ነዋ ...ለዛውም እንደፈለገው፡፡"
"እንቢ አልፈልግም ካለስ?"
"አንቺ ብቻ አምጪልኝ እንጂ በግድ ነው የምሰጠው..?"
‹‹እንግዲህ ተነሽ...ቃልዬ ልብሱን አወላልቆ ዝግጅ ሆኖ እየጠበቀሽ ነው...››
የእውነት ፈጥና መቀመጫዋን ለቃ ለመነሳት ብትሞክርም መቀመጫዋን ከሶፍው መላቀቅ አልቻለችም...ክንዷን ይዛ በመጎተት አስነሳቻትና እየጎተተች ማለት ይቻላል..ወደራሳቸው መኝታ ቤት ይዛት ገባች... መድህኔን ጠቅልላ እንዳስተኛችው ተኝቷል።
"የተኛ ሰው በማየቷ "ቃልዬ ነው እንዴ?"ስትል በተኮለታተፈ እና በተሰባበረ አረፍተ ነገር ጠየቀች፡፡
‹‹አዎ ግን በመስከርሽ እንዳይበሳጭ ድምፅሽን ቀንሺ አለቻት...በሁለት እጇ አፏን ፡አፈነች...አልጋው ጫፍ አስቀመጥኳት ‹‹...አሁን ልብስሽን ላውልቅልሽ..ተስማማሽ?›› ልክ እንደ መድህኔ እንዳደረገችው እያንዳንድን በሰውነቷ ላይ ያለውን ልብስ አወለቀችላትና መለመላዋን አስቀረቻት‹‹...ፐ ቅርፅ...›› በሚል አድናቆት እየጎተተች ከውስጥ አስገባቻት …እና ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብላ ‹‹እንግዲህ እኔ ሄድኩልሽ ..ያው ቃልዬ በደንብ ስጪው" አለቻት፡፡፡
መዲህኔ ላይ እየተጣበቀችበት‹‹ እ…ሺ ››.አለችን
መብራቱን አጠፍችና ከአልጋው ወረደች ..ተራመደችና ከክፍሉ አልወጣችም፤ እዛው መግቢያ ላይ ወዳለ ሶፍ ሄደችና ጋደም አለች...ከዛ የሚፈጠረውን ነገር መከታተል ጀመረች...
"ቃል አንተ ተኛህ እንዴ...?››ጊፍቲ ነች መድሀኔን እየወዘወዘች ያለችው፡፡
"አለው ....ልዪዬ"በሰመመን ውስጥ ሆኗ መለሰላት፡፡
"ከዛ የመተሻሸት ድምፅ ተሰማ ..ልዩ የሞባይሏን መብራት አበራችና ወደእነሱ አተኮረች ..ጊፍቲ እላዪ ላይ ወጥታበት ጎንበስ ብላ ከንፈሩን እየላሰችው ነው...ወገቧን ጨምቆ ይዞታል‹‹...ከደቂቃዎች በፊት ሁለቱም ተዝለፍልፈው እሬሳ መስለው አልነበረ እንዴ?›› ስትል በመገረም በውስጧ ጠየቀች፡፡ እንዲህ ልትል የቻለችው አንደኛው አንደኛውን ሲጨምቅና አንደኛው አንደኛውን በጥንካሬ ሲያንከባልል በማየቷ ነው....ከላይ አልብሳቸው የነበረ አልጋ ልብስም ሆነ ብርድ ልብስ ከላያቸው ተንሸራቶ ወደመሬት ወደቀ...አሁን ሁሉ ነገር በግልፅ ይታያት ጀመር...ሲተሻሹ..ሲሳሳሙ እና ሲዋሰብ በቂ የሆነ ፎቶም ቪዲዬም ቀረፀቻቸው፡፡.
ከዛ እነሱ እስኪረኩ መታገስ ከብዷት መሬት ካዝረከረኩት ልብስ ብድርብሱን ትታላቸው አልጋልብሱን ወሰደችና እሱን ተከናንባ እዛው ሶፋ ላይ ተኝች‹‹..እስቲ ሌሎች ሶስት መኝታ ክፍሎች ነበሩ ለምን እዛ ሄጄ አልተኛሁም..?››ስትል ጠየቀች…ምክንያቱን ግን አታውቀውም ነበር፡፡ወዲያው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት… ከእንቅልፏ ባና ሰዓቷን ሳታይ 12.10 ሆኖ ነበር..አይኗን አሻሽታ አልጋውን ስትመለከት ማመን አልቻለችም… ጊፍቲ መድሀኔ ክንድ ላይ ተንተርሳ አንደኛውን እግሩን ጭኖቾ መካከል ሰንቅሮ አንደኛውን ደግሞ ከላዬ ጭኖባት ጭልጥ ያለ እንቀለፍ ውስጥ ገብተው ያንኮራፋሉ… ማንኮራፋታቸው እራሱ ተራ በተራ ስለሆነ የራሱ የሆነ ስልተ ምት አለው….ከሶፋዋ ተነሳችና ቆመች.. .መኝታው ሰላልተመቻት ሰውነቷ ድቅቅ ብሏል…ተራመደች…ወደአልጋው ተጠጋችና እሪ ብላ ጩኸቷን ለቀቀችው……በመበርግ ሁለቱም ከእንቅልፋቸው ባነኑና ከተጣበቁበት ተላቀቁ፤ አንዴ እሷን አንዴ እርስ በረስ መተያየት ጀመሩ…፡፡
እሷ እንደድንቅ ብሄራዊ ተያትር ቤት ተዋናዬች ባጠናችውና በተዘጋጀችው መሰረት መድረኩን ተቆጠጣጠረችው፡
‹‹እንዴት እንዲህ ታደርጉኛላችሁ…ሰክራለች ብላችሁ እኔን ሶፋላ ላይ አስተኝታችሁ…?መድሀኒ ይሄ ለእኔ ይገባል.?››እራሷን ነጨች..ኸረ እንባዋ ሁሉ እየረገፈ ነው..መድሀኔ ተነስቶ ከአልጋው ወረደ… መለመላውን ሁለት ሴቶች ፊት ተገተረ….ጊፍቲ አንሶላውን ሰበሰበችና እርቃኖን ሸፈነች…ፊቷ በእፍረትና ግራ በመጋባት በአንዴ ሲገረጣ እየታየ ነው..
‹‹ልዩ ተረጋጊ …ምን እንደተፈጠረ በእውነት አላውቅም..››ወላል ላይ የተበታተነውን ልብሱን መሰብሰብ ጀመረ…ከመሀከል ፓንቱን እነሳና ለበሰ..፡፡
‹‹ሁለታችሁንም ከዛሬ ጀምሮ በአይኔ ማየት አልፈልግም….ያው ከመሀከላችሁ ወጥቼለሁ....እቤቱንም ተጋብታችሁ ልትኖሩበት ትችላላችሁ፡፡››
‹‹አረ ልዩ እንደዛ አይደለም…ይሄ ስህተት ነው››ጊፍቲ ነች እራሷን እንደምንም አበረታታ መናገር የጀመረችው፡፡
‹‹ምንም ስህተት አይደለም...እንደውም አሁን ሳስበው ይሄ ጉዳይ ከእኔም ሆነ ከቃል ጀርባ ሆናችሁ ስትፈፅሙት ዛሬ የመጀመሪያችሁ አይመስለኝም.››ነገሩን አንቦረቀቀችው፡፡
እንደ እብድ እየተወራጨችና እየተራገመች መኝታ ቤቱን ለቃ ወጣች፡፡ ሊለብስ ያዘጋጀውን ሱሪ በእጁ እንዳንከረፈፈ ሊከተላት ሞከረ….አልሰማችውም፡፡ ተንደርድራ ግቢውን ለቃ ወጣችና .ወዲያው ታክሲ ውስጥ ገባችና ከአካባቢው ተሰወረች…ስልኳን አጠፋችው፡፡
ቀጥታ ወደቤቷ ነው የሄደችው…..እናቷን እንኳን በቅጡ ሰላም ሳትል ወደ ክፍሏ ገባችና ከውስጥ ቀርቅሬ አልጋዋ ላይ ወጣች፡፡ድንግርግር ያለ ስሜት ነው እየተሰማት ያለው፡፡ ያሰበችውን ያህል ደስታ አልተሰማትም…ግን ቢሆንም ያሰበችውን በእቅዷ መሰረት ፈፅማዋለች....አሁን የሚቀራት ስህተቱን ተከትሎ መድህኔና ጊፊቲ ግንኙነታቸውን በዛው እንዲቀጥሉ ማድረግ ሲሆን በቀጣይነት ደግሞ ብቻውን የሚቀረውን ቃልን ብቻዋን ወደአለችው ወደራሷ ማምጣት…አዎ የመጨረሻ ግቧ ያ ነው፡፡አሁን መተኛት ስለፈለገች በአልጋ ልብሱ ሙሉ አካሏን ሸፈነች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ኬድሮን ከዕንቅልፋ የነቃችው 11 ሰዓት አካበቢ ቢሆንም መኝታ ቤቷን ለቃ ወደ በረንዳው የወጣችው 12 ሰዓት ተኩል ካለፈ በኋላ ነው፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ዘወትር እንደምታደርገው ዮጋ እየሰራች ነበር የቆየችው፡፡እቤቷን ለቃ ስትወጣ ንስሯ ተከትሏት ወጣ፡፡እሷ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ ማንበቧን ጀመረች ፡፡
ከ12 ሰዓት እስከሁለት ሰዓት ያለው ጊዜ ግቤዋ ውስጥ ባሉት ዛፎች ላይ የሰፈሩትን የተለያ አይነት የወፎች ህብረ ዝማሬ እየሰማች ንፁህ በሆነ አዕምሮዋ ተረጋግታ በተመስጦ የምታነብበት ሰዓት ነው፡፡ከሀገሯ ወጥታ ለገጣፎ ከከተመች በኃላ ያዳበረችው አዲስ ልምድ ንባብ ነው፡፡ከመፅሀፍቶች ጋር ያላት ቁርኝት ለእሷም ለራሷ እስኪገርማት ድረስ በጣም የጠነከረ ሆኗል፡፡በአጠቃላይ ሱሰኛ ሆናለች ፡፡
አንድ ሰዓት አካባቢ ከእሷ መኝታ ቤት ጎን ያለው የፕሮፌሰሩ በራፍ ተከፈተ ፡፡ያልጠበቀችው ክስተት ነበር፡፡ምክንያቱም ደግሞ የፕሮፌሰሩ ባህሪ ከእሷ የተለየ ስለሆነ ነው፡፡እሳቸው እሰከ ለሊቱ አስር ሰዓት ድረስ ይቆዩና የተለየ ፕሮግራም ከሌላቸው በስተቀር እስከ ጥዋቱ አራት ሰዓት ድረስ ይተኛሉ፡፡እና ስታነብ የነበረውን መጻሀፏን አጠፍ አድርጋ አይኗን ወደፕሮፌሰሩ በራፍ ላከች፡፡ከክፍሉ የወጡት ፕሮፌሰሩ ሳይሆኑ አንድ የ20 ዓመት አካባቢ ሚሆናት መልከ መልካም ሴት ነች፡፡ፈገግ አለች ፡፡
እኚ ሽማጊሌው ሙሁር ከአልማዝ የጠነከረ ጽናት እና የሚያስገርም ስብዕና ቢኖራቸውም ሴት ላይ ያላቸው አመል ግን የተለየ እና የሚገርም ነው፡፡ካሉበት ዕድሜ ጋር የሚቃረን አይነት ነው፡፡እሳቸው ግን ይሄንን ድክመታቸውን እንደድክመት ተመልክተውት አያውቁም፡፡ ለጤነኝነቴ እና በዚህ ዕድሜዬ ላይ ላለኝ ጥንካሬ ሚስጥሩ ሁለት ነው ፤የመጀመሪያው ከእጽዋት ጋር ያለኝ ፍቅር እና ቁርኝት ሲሆን ሌላው ደግሞ ለወሲብ ያለኝ ፍቅር ነው ብለው በድፍረት ለጠየቃቸው ሁሉ ይመልሳሉ፡፡ ጫን ብለው ለጠየቃቸውም ስለወሲብ ጥሩነት ዘርዘር አድርገው ለማስረዳት ይገደዳሉ‹‹…. የወሲብ ብቃት ቀጥታ ከጤነኝነት ጋር ትስስር አለው፣አንድ የወሲብ ብልቱ አልታዘዝ ያለው ሰው የሆነ የጓደለው ነገር አለው ማለት ነው፡፡ብዙ ጊዜ ትልቅ ቢዝነስ ሚያንቀሳሰቅሱ ባለሀብቶች ወይም ትልቅ ድርጅት ሚያሰተዳድሩ የስራ መሪዎች የወሲብ ስሜታቸው ሚቀሰቀሰው ከእለታቶች በአንድ ቀን ፤ለዛውም በብዙ ድካምና የመድሀኒት እገዛ ነው ፡፡ይህ የሚሆነበት ዋናው ምክንያት በጭንቀት የተበረዘ አዕምሮ እና በስራ የዛለ አካል ስላላቸው ነው ለወሲብ ዝግጁ መሆን የማይችሉት:: አልያም ድባቴ ውስጥ ገብተው በጭንቀት በሽታ እየተሰቃዩ ነው፡፡
ጥናተቶች አንደሚያመለክቱት የአንድ ሰው ብልቱ ሲቆም ያለው ጥንካሬ እና የልብ ጥንካሬ ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው…ተገትሮ የሚሰነጥቅ ብልት ያለው ወንድ ልቡም እንደዛው የተደራረበ ጠንካራና ከብረት የደደረ ነው፡፡ በሳምንት 4 ቀን ወሲብ የሚፈጽም ሰው ከማይፈጽም ሰው በልብ ድካም የመያዝ ዕድሉ 58 ፐርሰንት የበለጠ የተሻለ ነው ፡፡…..››እያሉ መሰል መረጃዎችን በመደርደር ያስረዳሉ፡፡
ስለእሳቸው ማሰቧን ገታ አድርጋ ፊት ለፊቷ ወዳለችው ልጅ ትኩረቷን መለሰች፡፡በዛ ተመሳሳይ ሰዓትም ንስሯ ፡፡ ከተቀመጠችበት ወንበር ትክክል ጣራው ላይ ሰፍሮ ዘና ብሎ ቁልቁል እሷንም ጊቢውንም እየቃኘ እና የጥዋቷን ፀሀይ አብሯት እየሞቀ እና የምትመለከታትን ልጅ እየተመለከተ ነው፡፡
ልጅቷ በራፉን መልሳ ዘጋችና ወደውጨኛው በራፍ ለመሄድ እርምጃ ስትጀምር አዕምሮዋን ሰረሰራት፡፡ቀና ብላ ወደ ንስሯ ስታይ እነዛ ሰርሰሪ አይኖቹን ልጅቷ ላይ ሰክቷል…‹‹ ነገር አለ›› አለችና እሷም ትኩረቷን በመሰብሰብ የሚያየየውን ለማየት ሞከረች…. የልጅቷ ልብ ጭልም ብሎ ነው እየታያት ያለው‹‹‹ ..በሀዘን ኩምትርትር ያለ….ደግሞ ግራ የተጋባ የተመሰቃቀለ ነፍስ ነው ያላቻት ›ስትለ አጉረመረመች.. ..ወጣቷ ቆንጆ ለሚያያት ሁሉ በፈገግታ የደመቀ ፊት ስለሚታየው በጨለማ የተሞላች ነፍስ አላት ተብሎ ቢነገረው ማንም አያምንም ፡፡
‹‹የእኔ እህት ››ብላ ጠራቻት
‹‹አቤት››አለችና ባለችበት ቆማ ፊቷን ወደ እሷ አዞረች…
‹‹ደህና አደርሽ …?››
‹‹ደህና ››አለች ግራ በመጋባት
‹‹ምነው በለሊት…?››
በንግግሯ ግራ ተጋብታ በእጇ የያዘችውን ሞባይል አብርታ አየችና‹‹እንድ ሰዓት እኮ ሆኗል…?››አለቻት፡፡
‹‹ካልቸኮልሽ ቁርስ አብረን እንብላና ትሄጄያለሽ›› …..ይህን ስትላት ልጅቱ እንደማትቸኩል እርግጠኛ ነኝ ….በቃ እንደውም የምትሄድበትም ያላት አይነት እንዳልሆነች ተረድታለች፡፡
እንደማቅማማት አለችና ፊቷን አዙራ ወደእሷ መጣች፤እንደዛ ያደረገችው ዝም ብላ አይደለም ….ውስጧ እንደዛ እንዳታደርግ ስለገፋፋት ነው…. ሁሌ ፕሮፌሰሩ የሚያመጧቸውን ሴቶች ወደ ክፍሏ በማስገባት ቁርስ እያበላች ትሸኛቸዋለች ማለት አይደለም፡፡በዛ ላይ እኮ ገና ቁርስም አልሰራችም፡፡ብቻ ይዛት ገባችና ቁጭ እንድትል ነገረቻት ..ያመለከተቻት ቦታ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ይቅርታ ቁርሱ አልተሰራም …ግን በፍጥነት ይደርሳል፡፡››ብላ እስቶቩን ለኮሰች
‹‹አረ ችግር የለም…››
ወደ ፊሪጅ አመራችና ከፍታ አንድ ብርጭቆ የማንጎ ጂውስ ሰጠቻት…… አመስግና ተቀበለቻትና መጠጣት ጀመረች ….እሷም እያወራቻት ቁርሱን መስራት ጀመረች…
‹‹እኔ ሶፊያ እባላለሁ…አንቺስ
…?››ሶፊያ የሚለውን ስም ለገጣፎ ከተመች ቡኃላ ደጋጋማ መጠቀም ጀምራለች፡፡ምንያቱም ከአዲስ ሰው ጋር ሁሉ ስትተዋወቅ ኬድሮን እባላለው ስትል‹‹ ኬድሮን ማለት ምን ማለት ነው?›› ብለው ሲጠየቋት እንዴት ብላ እንደምታስረዳ ግራ እየገባት ስለተቸገረች ነው፡ኬድሮን ማለት በማርስና በመሬት መካከል የሚገኝ ፕላኔት ነው ፤አባቴ የዛ ፕላኔት ኑዋሪ ነው…ትርጉሙ የዕውቀት ምድር ማለት ነው .እሱን ለማስታወስ ስትል እናቴ በፕላኔቷ ስም ስሜን ኬዴርን ብላ ሰየመችኝ ብላ ብታስረዳ‹‹እንዴ ኬድሮን የሚባል ፐላኔት መቼ ነው የተገኘው? ብለው ወደጎግል ይሮጣሉ… ምንም ሚጎለጎል መረጃ ሲያጡ እሷን እንደ እብድ ይመለከታቷል …ይሄ ነገር ሲደጋገምባት ሰለቻትና ለምን ሁለተኛ ስሜን አልጠቀምም አለችና ‹ሶፊያ› የሚል ስሞን አብዝታ መገልገል ጀመረች ፤እና ሁለቱንም ስሞቾን እንደአስፈላጊነቱ እየቀያየረች መጠቀም ጀመረች፡
‹‹አለም››
‹‹እሺ አለም….. አይዞሽ..ነገሮች ይስተካከላሉ››አለቻት፡፡
‹‹ ፍጥጥ ብላ አየቻት፡፡ምክንያቱም ስለታሪኳ ምንም አልነገረቻትም፡፡ እንዴት ልታውቅ ቻለች፤ ብላ ግራ ተጋብታ ነው፡፡››
‹‹አልገባኝም ››አለቻት፡፡
‹‹አይ አሁን ያለሽበት ችግር ይፈታል ማለቴ ነው››
በፍራቻም በጥርጣሬም እያየቻት ‹‹ነገርኩሽ እንዴ…? ››ጠየቀቻት …
‹‹አይ እንዲሁ ሳይሽ ውስጥሽ የተጨነቀ እንደሆነ ስለገባኝ ነው፡፡በጣም አዝነሻል፡፡››
እንባዋን መገደብ አቅቷት ዘረገፈችው፡፡
‹‹አዎ ከባድ ሀዘን ላይ ነኝ ፡፡››
‹‹አይዞሽ..እስኪ ንገሪኝ››
‹‹እንደምታስቢው ሸርሙጣ አይደለሁም…ይሄንን ስራ ከጀመርኩ ሳምንትም አይሆነኝም…››
‹‹አይዞሽ ..ተረጋጊና አጫውቺኝ››
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//
ኬድሮን ከዕንቅልፋ የነቃችው 11 ሰዓት አካበቢ ቢሆንም መኝታ ቤቷን ለቃ ወደ በረንዳው የወጣችው 12 ሰዓት ተኩል ካለፈ በኋላ ነው፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ዘወትር እንደምታደርገው ዮጋ እየሰራች ነበር የቆየችው፡፡እቤቷን ለቃ ስትወጣ ንስሯ ተከትሏት ወጣ፡፡እሷ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ ማንበቧን ጀመረች ፡፡
ከ12 ሰዓት እስከሁለት ሰዓት ያለው ጊዜ ግቤዋ ውስጥ ባሉት ዛፎች ላይ የሰፈሩትን የተለያ አይነት የወፎች ህብረ ዝማሬ እየሰማች ንፁህ በሆነ አዕምሮዋ ተረጋግታ በተመስጦ የምታነብበት ሰዓት ነው፡፡ከሀገሯ ወጥታ ለገጣፎ ከከተመች በኃላ ያዳበረችው አዲስ ልምድ ንባብ ነው፡፡ከመፅሀፍቶች ጋር ያላት ቁርኝት ለእሷም ለራሷ እስኪገርማት ድረስ በጣም የጠነከረ ሆኗል፡፡በአጠቃላይ ሱሰኛ ሆናለች ፡፡
አንድ ሰዓት አካባቢ ከእሷ መኝታ ቤት ጎን ያለው የፕሮፌሰሩ በራፍ ተከፈተ ፡፡ያልጠበቀችው ክስተት ነበር፡፡ምክንያቱም ደግሞ የፕሮፌሰሩ ባህሪ ከእሷ የተለየ ስለሆነ ነው፡፡እሳቸው እሰከ ለሊቱ አስር ሰዓት ድረስ ይቆዩና የተለየ ፕሮግራም ከሌላቸው በስተቀር እስከ ጥዋቱ አራት ሰዓት ድረስ ይተኛሉ፡፡እና ስታነብ የነበረውን መጻሀፏን አጠፍ አድርጋ አይኗን ወደፕሮፌሰሩ በራፍ ላከች፡፡ከክፍሉ የወጡት ፕሮፌሰሩ ሳይሆኑ አንድ የ20 ዓመት አካባቢ ሚሆናት መልከ መልካም ሴት ነች፡፡ፈገግ አለች ፡፡
እኚ ሽማጊሌው ሙሁር ከአልማዝ የጠነከረ ጽናት እና የሚያስገርም ስብዕና ቢኖራቸውም ሴት ላይ ያላቸው አመል ግን የተለየ እና የሚገርም ነው፡፡ካሉበት ዕድሜ ጋር የሚቃረን አይነት ነው፡፡እሳቸው ግን ይሄንን ድክመታቸውን እንደድክመት ተመልክተውት አያውቁም፡፡ ለጤነኝነቴ እና በዚህ ዕድሜዬ ላይ ላለኝ ጥንካሬ ሚስጥሩ ሁለት ነው ፤የመጀመሪያው ከእጽዋት ጋር ያለኝ ፍቅር እና ቁርኝት ሲሆን ሌላው ደግሞ ለወሲብ ያለኝ ፍቅር ነው ብለው በድፍረት ለጠየቃቸው ሁሉ ይመልሳሉ፡፡ ጫን ብለው ለጠየቃቸውም ስለወሲብ ጥሩነት ዘርዘር አድርገው ለማስረዳት ይገደዳሉ‹‹…. የወሲብ ብቃት ቀጥታ ከጤነኝነት ጋር ትስስር አለው፣አንድ የወሲብ ብልቱ አልታዘዝ ያለው ሰው የሆነ የጓደለው ነገር አለው ማለት ነው፡፡ብዙ ጊዜ ትልቅ ቢዝነስ ሚያንቀሳሰቅሱ ባለሀብቶች ወይም ትልቅ ድርጅት ሚያሰተዳድሩ የስራ መሪዎች የወሲብ ስሜታቸው ሚቀሰቀሰው ከእለታቶች በአንድ ቀን ፤ለዛውም በብዙ ድካምና የመድሀኒት እገዛ ነው ፡፡ይህ የሚሆነበት ዋናው ምክንያት በጭንቀት የተበረዘ አዕምሮ እና በስራ የዛለ አካል ስላላቸው ነው ለወሲብ ዝግጁ መሆን የማይችሉት:: አልያም ድባቴ ውስጥ ገብተው በጭንቀት በሽታ እየተሰቃዩ ነው፡፡
ጥናተቶች አንደሚያመለክቱት የአንድ ሰው ብልቱ ሲቆም ያለው ጥንካሬ እና የልብ ጥንካሬ ቀጥተኛ ግንኙነት አላቸው…ተገትሮ የሚሰነጥቅ ብልት ያለው ወንድ ልቡም እንደዛው የተደራረበ ጠንካራና ከብረት የደደረ ነው፡፡ በሳምንት 4 ቀን ወሲብ የሚፈጽም ሰው ከማይፈጽም ሰው በልብ ድካም የመያዝ ዕድሉ 58 ፐርሰንት የበለጠ የተሻለ ነው ፡፡…..››እያሉ መሰል መረጃዎችን በመደርደር ያስረዳሉ፡፡
ስለእሳቸው ማሰቧን ገታ አድርጋ ፊት ለፊቷ ወዳለችው ልጅ ትኩረቷን መለሰች፡፡በዛ ተመሳሳይ ሰዓትም ንስሯ ፡፡ ከተቀመጠችበት ወንበር ትክክል ጣራው ላይ ሰፍሮ ዘና ብሎ ቁልቁል እሷንም ጊቢውንም እየቃኘ እና የጥዋቷን ፀሀይ አብሯት እየሞቀ እና የምትመለከታትን ልጅ እየተመለከተ ነው፡፡
ልጅቷ በራፉን መልሳ ዘጋችና ወደውጨኛው በራፍ ለመሄድ እርምጃ ስትጀምር አዕምሮዋን ሰረሰራት፡፡ቀና ብላ ወደ ንስሯ ስታይ እነዛ ሰርሰሪ አይኖቹን ልጅቷ ላይ ሰክቷል…‹‹ ነገር አለ›› አለችና እሷም ትኩረቷን በመሰብሰብ የሚያየየውን ለማየት ሞከረች…. የልጅቷ ልብ ጭልም ብሎ ነው እየታያት ያለው‹‹‹ ..በሀዘን ኩምትርትር ያለ….ደግሞ ግራ የተጋባ የተመሰቃቀለ ነፍስ ነው ያላቻት ›ስትለ አጉረመረመች.. ..ወጣቷ ቆንጆ ለሚያያት ሁሉ በፈገግታ የደመቀ ፊት ስለሚታየው በጨለማ የተሞላች ነፍስ አላት ተብሎ ቢነገረው ማንም አያምንም ፡፡
‹‹የእኔ እህት ››ብላ ጠራቻት
‹‹አቤት››አለችና ባለችበት ቆማ ፊቷን ወደ እሷ አዞረች…
‹‹ደህና አደርሽ …?››
‹‹ደህና ››አለች ግራ በመጋባት
‹‹ምነው በለሊት…?››
በንግግሯ ግራ ተጋብታ በእጇ የያዘችውን ሞባይል አብርታ አየችና‹‹እንድ ሰዓት እኮ ሆኗል…?››አለቻት፡፡
‹‹ካልቸኮልሽ ቁርስ አብረን እንብላና ትሄጄያለሽ›› …..ይህን ስትላት ልጅቱ እንደማትቸኩል እርግጠኛ ነኝ ….በቃ እንደውም የምትሄድበትም ያላት አይነት እንዳልሆነች ተረድታለች፡፡
እንደማቅማማት አለችና ፊቷን አዙራ ወደእሷ መጣች፤እንደዛ ያደረገችው ዝም ብላ አይደለም ….ውስጧ እንደዛ እንዳታደርግ ስለገፋፋት ነው…. ሁሌ ፕሮፌሰሩ የሚያመጧቸውን ሴቶች ወደ ክፍሏ በማስገባት ቁርስ እያበላች ትሸኛቸዋለች ማለት አይደለም፡፡በዛ ላይ እኮ ገና ቁርስም አልሰራችም፡፡ብቻ ይዛት ገባችና ቁጭ እንድትል ነገረቻት ..ያመለከተቻት ቦታ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ይቅርታ ቁርሱ አልተሰራም …ግን በፍጥነት ይደርሳል፡፡››ብላ እስቶቩን ለኮሰች
‹‹አረ ችግር የለም…››
ወደ ፊሪጅ አመራችና ከፍታ አንድ ብርጭቆ የማንጎ ጂውስ ሰጠቻት…… አመስግና ተቀበለቻትና መጠጣት ጀመረች ….እሷም እያወራቻት ቁርሱን መስራት ጀመረች…
‹‹እኔ ሶፊያ እባላለሁ…አንቺስ
…?››ሶፊያ የሚለውን ስም ለገጣፎ ከተመች ቡኃላ ደጋጋማ መጠቀም ጀምራለች፡፡ምንያቱም ከአዲስ ሰው ጋር ሁሉ ስትተዋወቅ ኬድሮን እባላለው ስትል‹‹ ኬድሮን ማለት ምን ማለት ነው?›› ብለው ሲጠየቋት እንዴት ብላ እንደምታስረዳ ግራ እየገባት ስለተቸገረች ነው፡ኬድሮን ማለት በማርስና በመሬት መካከል የሚገኝ ፕላኔት ነው ፤አባቴ የዛ ፕላኔት ኑዋሪ ነው…ትርጉሙ የዕውቀት ምድር ማለት ነው .እሱን ለማስታወስ ስትል እናቴ በፕላኔቷ ስም ስሜን ኬዴርን ብላ ሰየመችኝ ብላ ብታስረዳ‹‹እንዴ ኬድሮን የሚባል ፐላኔት መቼ ነው የተገኘው? ብለው ወደጎግል ይሮጣሉ… ምንም ሚጎለጎል መረጃ ሲያጡ እሷን እንደ እብድ ይመለከታቷል …ይሄ ነገር ሲደጋገምባት ሰለቻትና ለምን ሁለተኛ ስሜን አልጠቀምም አለችና ‹ሶፊያ› የሚል ስሞን አብዝታ መገልገል ጀመረች ፤እና ሁለቱንም ስሞቾን እንደአስፈላጊነቱ እየቀያየረች መጠቀም ጀመረች፡
‹‹አለም››
‹‹እሺ አለም….. አይዞሽ..ነገሮች ይስተካከላሉ››አለቻት፡፡
‹‹ ፍጥጥ ብላ አየቻት፡፡ምክንያቱም ስለታሪኳ ምንም አልነገረቻትም፡፡ እንዴት ልታውቅ ቻለች፤ ብላ ግራ ተጋብታ ነው፡፡››
‹‹አልገባኝም ››አለቻት፡፡
‹‹አይ አሁን ያለሽበት ችግር ይፈታል ማለቴ ነው››
በፍራቻም በጥርጣሬም እያየቻት ‹‹ነገርኩሽ እንዴ…? ››ጠየቀቻት …
‹‹አይ እንዲሁ ሳይሽ ውስጥሽ የተጨነቀ እንደሆነ ስለገባኝ ነው፡፡በጣም አዝነሻል፡፡››
እንባዋን መገደብ አቅቷት ዘረገፈችው፡፡
‹‹አዎ ከባድ ሀዘን ላይ ነኝ ፡፡››
‹‹አይዞሽ..እስኪ ንገሪኝ››
‹‹እንደምታስቢው ሸርሙጣ አይደለሁም…ይሄንን ስራ ከጀመርኩ ሳምንትም አይሆነኝም…››
‹‹አይዞሽ ..ተረጋጊና አጫውቺኝ››
‹‹በነገራችን ላይ ወደሀገር የገባሁትም የዛሬ ወር አካባቢ ነው፡፡ላለፉት ሶስት አመታት ሳውዲ ነበርኩ…በህገወጥ መልኩ ስለሄድኩ በመሹለክለክ ነበር የኖርኩት… የቀን ጎዶሎ ግን ከሶስት ወር በፊት ከቀጣሪዬ ማዳም ጋር ተጣላሁና አስያዘችኝ››
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሀዋሳ
ሁሴን ወደ ሲዩዘርላንድ ከበረረ ሀያ ቀን አልፎታል፡፡ያለፉትን ሀያ ቀናት የእሱንም ቦታ ተክታ ለስራው ከላይ እታች በመሯሯጥ ብታሳልፍም ከናፍቆት ግን ማምለጥ አልቻለችም፡፡አዎ ሁሴን ባልተለመደ መልኩ በጣም ናፍቋታል፡፡እራሷን በሌላ ሰው ህልውና ላይ ይሄን ያህል መለጠፍ አትፈልግም ነበር፤ምንም ቋሚና ዘላቂ ነገር እንደሌለ ህይወት ደጋግማ አስተምራታለች፡፡የእኔ የምትለው ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሰላምም ሆነ በአደጋ ብቻ በሆነ ምክንያት እንደሚለያትና ለዛም ዝግጁ ሆና መጠበቅ እንዳለባት የዘወትር መፈክሯና መመሪያዋ ነበር፡፡አሁን ግን መልሳ ደከመች፤እናም ባሏ ናፈቃት፡፡እለቱ ሰንበት ስለሆነ የቤቷ ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዢን እየተመለከተች ነው፡፡
አይድል ፕሮግራም..በሀዋሳ የሚካሄድ የማጣሪያ ውድድር እየተመለከተች ነው፡፡
በአብረሀም ወልዴ የሚመራው የዳኞች ቡድን
የዳኝነት ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል ወደ መድረክ እየወጡ የተዘጋጁበትን ዘፈን በመዝፈን ተፈጥሮ
የቸረቻቸውን ድምጽና በጥረታቸው ያደበሩትን
ችሎታ በማዋሀድ ዳኞቹንም ሆነ ተመልካቾችን
በማሳመን ለአዲስአበባው ውድድር ለማለፍ ይጥራሉ፡፡ጥቂቶች ይሳካላቸዋል ፤ሌሎቹ ደግሞ አንገት ደፍተውና ፈዘው ከመድረኩ
ይሰናበታሉ፡፡ትንግርት ሁሌ ይህን ፕሮግራም ስታይ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የሚሰማት፡፡
ዘና የሚያደርገት እንዳለ ሁሉ የሚያሳዝኗትም
ተወዳዳሪዎች አሉ፡፡ከችሎታቸው በላይ
ጉጉታቸው የናረ፣ብዙ ተስፋ አድርገው መጥተው በዳኞቹ ቁርጥ ያለ ሞያዊ
አስተያየት ሽምቅቅ የሚሉ ወጣት ጨቅላዎች፤ ያሳዝኗታል፡፡ችሎታው እያላቸውም ፍራቻቸውን ብቻ ማሸነፍ ተስኗቸው ያላቸውን ነገር መግለጽ ባለመቻላቸው አጉል የሚሆኑም አሉ፤እነሱም ያሳዝኗታል፡፡
...አሁን ግን እያየች ያለቻው ድንቅና የሚያስደምም ችሎታ ነው፡፡አስር ሁለት አመት የማይበልጣቸው ሁለት ሴት ልጆች ናቸው የሚታዩት፡፡አንደኛዋ ጊታሯን ይዛ የተዘጋጀላት መቀመጫ ላይ ተቀመጠችና በጣቶቿ የጊታሩን ክሮች በመነካካት ፈታተሸች፤ሌለኛዋ ከፊት ለፊቷ በሜትሮች ርቀት ማይኩን ይዛ ::
አብረሀም ወልዴ መናገር ጀመረ....
‹‹እሺ እንኳን በሰላም መጣችሁ እያልኩ እራሳችሁን እንድታስተዋውቁ ዕድሉን ልስጣችሁ ፡፡››
‹‹ስሜ ሀሊማ ታዲዬስ ይባላል፡፡ የምጫወትላችሁ የተፈራ ካሳን ‹አባብዬ› የሚለውን ዘፈን ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው፡፡ባለጊታሯስ ስምሽ ማነው ?››
‹‹ስሜ ሄለን ታዲዬስ ይባላል፤ጊታርና ፒያኖ ተጨዋች ነኝ።
<<እህት አማቾች ናችሁ ?››አረጋኸኝ መሀከል ገብቶ ጠየቀ፡፡
‹‹አዎ እህቴ ናት፡፡››
ይሄ ሁሉ ሲሆን ትንግርት ስትከታተል የነበረው በግማሽ ልቧ ነበር፡፡እህትማማቾች ነን ሲሉ ግን ትንሽ ግር አላት፡፡በእኩል ዕድሜ ላይ ናቸው፡፡የትኛዋ ታላቅ የትኛዋ ደግሞ ታናሽ ትሆን? ስትል እራሷን ጥያቄ ጠየቀች፡፡ ደግሞ ምናቸውም አይመሳሰልም <<የእናት ሆድ ዥንጉርጉር›› ይባል የለ ብላ ለራሷ መልስ ሰጠች፡፡
‹‹በሉ ቀጥሉ..መልካም ዕድል፡፡››ከዳኞቹ ፍቃድ አገኙ፡፡
ሄለን እነዛ ቀጫጭንና ለጋ ጣቶቾን የጊታሩ ክሮች ላይ ማርመስመስ ጀመረች ፡፡ የሙዚቃ መሳሪያውን ምት ተከትሎ የሀሊማ ተስረቅራቂና ማራኪ ድምጽ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ በአዳራሹ የሞላው ተመልካች ብቻ ሳይሆን በየቤቱ በቲቪ ፕሮግራሙን የሚከታተለው ህዝብም ፀጥ የሚያሰኝ አደንዛዥ ድምጽ ነበር፡፡በዚህ ዕድሜ በእንዲህ አይነት ችሎታ? እንዴት ነው በዚህ ዕድሜ የሙዚቃ መሳሪያን ስልተ-ምት ጠብቆ ስይደናገሩና ሳይንሸራተቱ በዚህ ልክ መዝፈን የቻሉት?፡፡
ዳኞቹ ሳይቀር አፋቸውን ከፈቱ፡፡ደግሞ በሙዚቃው ሁለቱም ጉንጮች ላይ እንባ እየተንጠባጠበ ነው፡፡ሲጨርሱ የአዳራሹ ሰው ሁሉ አረንጎዴ ካርዱን እያወዛወዘ ከመቀመጨው ተነሳ፡፡ደኞቹም እያጨበጨቡ ቆሙ .. መድረክ ድረስ በመሄድ በየተራ አቅፈው ሳሟቸው፡፡
አስተያየት መስጠት ተጀመረ..የመጀመሪያው ዳኛ
‹‹በእውነት ሀዋሳ እናንተን የመሰሉ ባለድንቅ ችሎታ ሙዚቀኞችን ስላፈራች እድለኛ ነች፡፡
እኛም እዚህ መጥተን እናንተን ስላገኘን እድለኞች ነን፤በቃ ልዩ ናችሁ፡፡››
ሁለተኛው ዳኛ…..
‹‹ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ሙዚቃው ከህይወታችሁ ጋር የሚያይዘው ጉዳይ አለ? ሁለታችሁም ስታለቅሱ ነበር፡፡እኔንም አስለቅሳችሁኛል፡፡ምከንያት ነበራችሁ?››
ሀሊማ መናገር ጀመረች‹‹አዎ ሁለታቸንም አባታችንን በጣም እንወደዋለን፡፡እርግጥ ሁሉም ሰው አባቱን በጣም ይወዳል፡፡እመኑን የእኛ አባት ግን ልዩ ሰው ነው፡፡›› አዳራሹ በሳቅና በጭብጨባ ተናጋ፡፡
ሄለን ቀጠለች‹‹ታዲያ አንተ አባታችን ባትሆን ኖሮ እኛ ዛሬ እንዲህ አምሮብን ሙዚቃ እየተጫወትን እንዲህ አዳራሽ ሙሉ ህዝብ እያጨበጨበልን አንታይም ነበር.፡፡ምክንያም እድሉም ጊዜውም አይኖረንም ነበር፡፡አዎ አባት ባትሆነን ኖሮ ይሄኔ ሁለታችንም አሞራ ገደል
አካባቢ ከሚገኝ ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ ተበላሽቶ የተጣለ ምግብ ከቆሻሻው በመለየት በመመገብ ላይ ነበርን፡፡…እና ከእንደገና ስለፈጠርከን አመሰግናለሁ ...ታዲ እንወድሀለን፡፡››
ዳኞቹም ታዳሚዎቹም ከልጆቹ ችሎታ በላይ በንግግራቸው ድንግርግር እንዳሉ ፊታቸውን በመመልከት ማወቅ ይቻላል፡፡
‹‹እባክህ አቶ ታዲዬስ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ካላህ ወደ መድረክ ወጥተህ አንድ ነገር በለን››ከዳኞቹ መካከል አንድ ተናገረ፡፡ በአዳራሹ ያላው ታዳሚ እርስ በርሱ ዞር ዞር በማለት መተያየት ጀመረ፡፡ከመቀመጫው ተነስቶ ወደ መድረክ የሚወጣ ሰው ለመመልከት፡፡
‹‹ታዲ ና እንጂ››ሄለን ከመድረክ ተማፀነች፡፡
የሁለት ልጆች አባት ሳይሆን ተደባበዳቢ ቦዴ ጋርድ የሚመስል ጠይም ደንዳና ወጣት ወደ መድረኩ ወጣና ሁለቱንም ልጆቹን አቅፎ
ጉንጮቻቸውን ከሳመ በኃላ ማይኩን ተቀብሎ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ታዴዬስ ማለት እኔ ነኝ፡፡ልጆቼ
ስለእኔ ያሉት ትንሽ ተጋኗል፡፡እውነታው በተቃራኒው ነው፡፡እነሱ ልጆቼ በመሆናቸው
በአሁኑ ወቅት በአለም በጣም እድለኛው ሰው
እኔ ነኝ፡፡ምን አልባት ችሎታቸውን አይታችሁ
ስታጨበጭቡላቸው ነበር፡፡ግን እመኑኝ መድረክ የመጀመሪያ ቀናቸው ስለሆነ የችሎታቸውን ግማሽም አላሳዮችሁም...እናም
ሁላችሁም እዚህ አዳራሹን የሞላችሁ ሁሉ ብትቀኑብኝ አይገርመኝም፡፡ምክንያቱም እኔ የእነዚህ ዕንቁ ልጆች አባት ነኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡>> ብሎ ወረደ፡፡ፕሮግራሙ ቢያልቅም ትንግርት
ስለልጆቹም ሆነ ስለአባትዬው ልትረሳ
አልቻለችም፡፡የሆነ ያልተለመደ ነገር ነው
የሆነባት፡፡<<አባታችን ባትሆን የቆሻሻ ገንዳ ላይ
ምግብ እንለቃቅም ነበር›› ሲሉ ምን ማለታቸው ነው?ግን የእውነት አባታቸው ነው ?
አልመሰላትም፡፡እንዴት አድርጎ ቢያሳድጋቸው
ነው በዚህ መጠን ሊወዱት የቻሉት?እውነትም
እሱ እንዳለው የሚቀናበት አባት ነው ? አለችና ቲቪውን አጥፍታ አየር ለመቀበል ቤቷን ለቃ ወደ ውጭ ወጣች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች እያደረጋቹ አደለም በየቀኑ ለመልቀቅ እየሞከርኩ ነው እናንተም ማበረታታችሁን ቀጥሉ አመሰጎናለሁ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሀዋሳ
ሁሴን ወደ ሲዩዘርላንድ ከበረረ ሀያ ቀን አልፎታል፡፡ያለፉትን ሀያ ቀናት የእሱንም ቦታ ተክታ ለስራው ከላይ እታች በመሯሯጥ ብታሳልፍም ከናፍቆት ግን ማምለጥ አልቻለችም፡፡አዎ ሁሴን ባልተለመደ መልኩ በጣም ናፍቋታል፡፡እራሷን በሌላ ሰው ህልውና ላይ ይሄን ያህል መለጠፍ አትፈልግም ነበር፤ምንም ቋሚና ዘላቂ ነገር እንደሌለ ህይወት ደጋግማ አስተምራታለች፡፡የእኔ የምትለው ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሰላምም ሆነ በአደጋ ብቻ በሆነ ምክንያት እንደሚለያትና ለዛም ዝግጁ ሆና መጠበቅ እንዳለባት የዘወትር መፈክሯና መመሪያዋ ነበር፡፡አሁን ግን መልሳ ደከመች፤እናም ባሏ ናፈቃት፡፡እለቱ ሰንበት ስለሆነ የቤቷ ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዢን እየተመለከተች ነው፡፡
አይድል ፕሮግራም..በሀዋሳ የሚካሄድ የማጣሪያ ውድድር እየተመለከተች ነው፡፡
በአብረሀም ወልዴ የሚመራው የዳኞች ቡድን
የዳኝነት ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል ወደ መድረክ እየወጡ የተዘጋጁበትን ዘፈን በመዝፈን ተፈጥሮ
የቸረቻቸውን ድምጽና በጥረታቸው ያደበሩትን
ችሎታ በማዋሀድ ዳኞቹንም ሆነ ተመልካቾችን
በማሳመን ለአዲስአበባው ውድድር ለማለፍ ይጥራሉ፡፡ጥቂቶች ይሳካላቸዋል ፤ሌሎቹ ደግሞ አንገት ደፍተውና ፈዘው ከመድረኩ
ይሰናበታሉ፡፡ትንግርት ሁሌ ይህን ፕሮግራም ስታይ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የሚሰማት፡፡
ዘና የሚያደርገት እንዳለ ሁሉ የሚያሳዝኗትም
ተወዳዳሪዎች አሉ፡፡ከችሎታቸው በላይ
ጉጉታቸው የናረ፣ብዙ ተስፋ አድርገው መጥተው በዳኞቹ ቁርጥ ያለ ሞያዊ
አስተያየት ሽምቅቅ የሚሉ ወጣት ጨቅላዎች፤ ያሳዝኗታል፡፡ችሎታው እያላቸውም ፍራቻቸውን ብቻ ማሸነፍ ተስኗቸው ያላቸውን ነገር መግለጽ ባለመቻላቸው አጉል የሚሆኑም አሉ፤እነሱም ያሳዝኗታል፡፡
...አሁን ግን እያየች ያለቻው ድንቅና የሚያስደምም ችሎታ ነው፡፡አስር ሁለት አመት የማይበልጣቸው ሁለት ሴት ልጆች ናቸው የሚታዩት፡፡አንደኛዋ ጊታሯን ይዛ የተዘጋጀላት መቀመጫ ላይ ተቀመጠችና በጣቶቿ የጊታሩን ክሮች በመነካካት ፈታተሸች፤ሌለኛዋ ከፊት ለፊቷ በሜትሮች ርቀት ማይኩን ይዛ ::
አብረሀም ወልዴ መናገር ጀመረ....
‹‹እሺ እንኳን በሰላም መጣችሁ እያልኩ እራሳችሁን እንድታስተዋውቁ ዕድሉን ልስጣችሁ ፡፡››
‹‹ስሜ ሀሊማ ታዲዬስ ይባላል፡፡ የምጫወትላችሁ የተፈራ ካሳን ‹አባብዬ› የሚለውን ዘፈን ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው፡፡ባለጊታሯስ ስምሽ ማነው ?››
‹‹ስሜ ሄለን ታዲዬስ ይባላል፤ጊታርና ፒያኖ ተጨዋች ነኝ።
<<እህት አማቾች ናችሁ ?››አረጋኸኝ መሀከል ገብቶ ጠየቀ፡፡
‹‹አዎ እህቴ ናት፡፡››
ይሄ ሁሉ ሲሆን ትንግርት ስትከታተል የነበረው በግማሽ ልቧ ነበር፡፡እህትማማቾች ነን ሲሉ ግን ትንሽ ግር አላት፡፡በእኩል ዕድሜ ላይ ናቸው፡፡የትኛዋ ታላቅ የትኛዋ ደግሞ ታናሽ ትሆን? ስትል እራሷን ጥያቄ ጠየቀች፡፡ ደግሞ ምናቸውም አይመሳሰልም <<የእናት ሆድ ዥንጉርጉር›› ይባል የለ ብላ ለራሷ መልስ ሰጠች፡፡
‹‹በሉ ቀጥሉ..መልካም ዕድል፡፡››ከዳኞቹ ፍቃድ አገኙ፡፡
ሄለን እነዛ ቀጫጭንና ለጋ ጣቶቾን የጊታሩ ክሮች ላይ ማርመስመስ ጀመረች ፡፡ የሙዚቃ መሳሪያውን ምት ተከትሎ የሀሊማ ተስረቅራቂና ማራኪ ድምጽ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ በአዳራሹ የሞላው ተመልካች ብቻ ሳይሆን በየቤቱ በቲቪ ፕሮግራሙን የሚከታተለው ህዝብም ፀጥ የሚያሰኝ አደንዛዥ ድምጽ ነበር፡፡በዚህ ዕድሜ በእንዲህ አይነት ችሎታ? እንዴት ነው በዚህ ዕድሜ የሙዚቃ መሳሪያን ስልተ-ምት ጠብቆ ስይደናገሩና ሳይንሸራተቱ በዚህ ልክ መዝፈን የቻሉት?፡፡
ዳኞቹ ሳይቀር አፋቸውን ከፈቱ፡፡ደግሞ በሙዚቃው ሁለቱም ጉንጮች ላይ እንባ እየተንጠባጠበ ነው፡፡ሲጨርሱ የአዳራሹ ሰው ሁሉ አረንጎዴ ካርዱን እያወዛወዘ ከመቀመጨው ተነሳ፡፡ደኞቹም እያጨበጨቡ ቆሙ .. መድረክ ድረስ በመሄድ በየተራ አቅፈው ሳሟቸው፡፡
አስተያየት መስጠት ተጀመረ..የመጀመሪያው ዳኛ
‹‹በእውነት ሀዋሳ እናንተን የመሰሉ ባለድንቅ ችሎታ ሙዚቀኞችን ስላፈራች እድለኛ ነች፡፡
እኛም እዚህ መጥተን እናንተን ስላገኘን እድለኞች ነን፤በቃ ልዩ ናችሁ፡፡››
ሁለተኛው ዳኛ…..
‹‹ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ሙዚቃው ከህይወታችሁ ጋር የሚያይዘው ጉዳይ አለ? ሁለታችሁም ስታለቅሱ ነበር፡፡እኔንም አስለቅሳችሁኛል፡፡ምከንያት ነበራችሁ?››
ሀሊማ መናገር ጀመረች‹‹አዎ ሁለታቸንም አባታችንን በጣም እንወደዋለን፡፡እርግጥ ሁሉም ሰው አባቱን በጣም ይወዳል፡፡እመኑን የእኛ አባት ግን ልዩ ሰው ነው፡፡›› አዳራሹ በሳቅና በጭብጨባ ተናጋ፡፡
ሄለን ቀጠለች‹‹ታዲያ አንተ አባታችን ባትሆን ኖሮ እኛ ዛሬ እንዲህ አምሮብን ሙዚቃ እየተጫወትን እንዲህ አዳራሽ ሙሉ ህዝብ እያጨበጨበልን አንታይም ነበር.፡፡ምክንያም እድሉም ጊዜውም አይኖረንም ነበር፡፡አዎ አባት ባትሆነን ኖሮ ይሄኔ ሁለታችንም አሞራ ገደል
አካባቢ ከሚገኝ ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ ተበላሽቶ የተጣለ ምግብ ከቆሻሻው በመለየት በመመገብ ላይ ነበርን፡፡…እና ከእንደገና ስለፈጠርከን አመሰግናለሁ ...ታዲ እንወድሀለን፡፡››
ዳኞቹም ታዳሚዎቹም ከልጆቹ ችሎታ በላይ በንግግራቸው ድንግርግር እንዳሉ ፊታቸውን በመመልከት ማወቅ ይቻላል፡፡
‹‹እባክህ አቶ ታዲዬስ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ካላህ ወደ መድረክ ወጥተህ አንድ ነገር በለን››ከዳኞቹ መካከል አንድ ተናገረ፡፡ በአዳራሹ ያላው ታዳሚ እርስ በርሱ ዞር ዞር በማለት መተያየት ጀመረ፡፡ከመቀመጫው ተነስቶ ወደ መድረክ የሚወጣ ሰው ለመመልከት፡፡
‹‹ታዲ ና እንጂ››ሄለን ከመድረክ ተማፀነች፡፡
የሁለት ልጆች አባት ሳይሆን ተደባበዳቢ ቦዴ ጋርድ የሚመስል ጠይም ደንዳና ወጣት ወደ መድረኩ ወጣና ሁለቱንም ልጆቹን አቅፎ
ጉንጮቻቸውን ከሳመ በኃላ ማይኩን ተቀብሎ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ታዴዬስ ማለት እኔ ነኝ፡፡ልጆቼ
ስለእኔ ያሉት ትንሽ ተጋኗል፡፡እውነታው በተቃራኒው ነው፡፡እነሱ ልጆቼ በመሆናቸው
በአሁኑ ወቅት በአለም በጣም እድለኛው ሰው
እኔ ነኝ፡፡ምን አልባት ችሎታቸውን አይታችሁ
ስታጨበጭቡላቸው ነበር፡፡ግን እመኑኝ መድረክ የመጀመሪያ ቀናቸው ስለሆነ የችሎታቸውን ግማሽም አላሳዮችሁም...እናም
ሁላችሁም እዚህ አዳራሹን የሞላችሁ ሁሉ ብትቀኑብኝ አይገርመኝም፡፡ምክንያቱም እኔ የእነዚህ ዕንቁ ልጆች አባት ነኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡>> ብሎ ወረደ፡፡ፕሮግራሙ ቢያልቅም ትንግርት
ስለልጆቹም ሆነ ስለአባትዬው ልትረሳ
አልቻለችም፡፡የሆነ ያልተለመደ ነገር ነው
የሆነባት፡፡<<አባታችን ባትሆን የቆሻሻ ገንዳ ላይ
ምግብ እንለቃቅም ነበር›› ሲሉ ምን ማለታቸው ነው?ግን የእውነት አባታቸው ነው ?
አልመሰላትም፡፡እንዴት አድርጎ ቢያሳድጋቸው
ነው በዚህ መጠን ሊወዱት የቻሉት?እውነትም
እሱ እንዳለው የሚቀናበት አባት ነው ? አለችና ቲቪውን አጥፍታ አየር ለመቀበል ቤቷን ለቃ ወደ ውጭ ወጣች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች እያደረጋቹ አደለም በየቀኑ ለመልቀቅ እየሞከርኩ ነው እናንተም ማበረታታችሁን ቀጥሉ አመሰጎናለሁ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ:
….
‹‹ምነው አልክ..?ፒጃማ የለህም እንዴ?››
‹‹አለኝ ግን በማሳጁ ምን ያህል ብቁ ሆነሻል.ስልጠናውስ እንዴት ነበር? የሚለውን ማወቅ እፈልጋለሁ…››
‹‹ተው… እርግጠኛ ነህ?››
‹‹አዎ ምነው ፈራሽ አንዴ.?ነው ወይስ በብቃትሽ አትተማመኝም? እንዳዛ ከሆነ ይቅር፡› ብሎ ፊቱን ወደቁምሳጥኑ መልሶ ሊራመድ ሲል እጁን ለቀም አደረገችውና‹‹መፍራት ያለብህማ አንተ ነህ…ትዝ ይልሀል ያን ቀን ቤትህ አታለህ አስገብተኸኝ የዋህነቴን ተጠቅመህ እዛ የማሳጅ ጠረጴዛ ላይ አስተኝተህ እንዴት እንደተጫወትክብኝ ያንን መበቀል መቻል አለብኝ፡፡›› ብላ እየጎተተች ወደ ማሳጅ ጠረጴዛው ወሰደችና በጀርባው እንዲተኛ አደረገችው፡፡
ከዛ በቅርብ ካለው ቅባት ወደተኮለኮለበት ጠረጴዛ በመሄድ አንዱን መርጣ አነሳችና ጀርባው ላይ አፈሰሰችበትና ከላይ ከጆሮ ግንዱ ጀምራ እስከታች የእግር ጣቶቹ ድረስ በወሰደችው ሰልጠና መሰረት የተለያዩ ቴክኒኮችን በመጠቀመ እያገለባበጠች ለአርባ ደቂቃ ካሸችው በኃላ እጅግ በሚገርም ሰመመንና መመሰጥ ውስጥ ገብቶ ከተዝለፈለፈ በኃላ እንደምንም ከጠረጴዛው ላይ አስነስታ ወለሉ ላይ ዘረረችው…. ከዛማ ቀሚሷን ወደላይ መዥርጣ አውልቃ ከጎኑ ተኛች…ከዛ በኋላ የነበረውን ለማሰብም ይከብዳታል…ያንን ሰፊ የመኝታ ቤት ወለል እየተንከባለሉበት አንዴ የአልጋው ጠርዝ ሲገጫቸው፤አንዴ ከጠረጴዛው እግር ጋር ሲላተሙ አንዴ ስትገለብጠው….ከዛም ሲገለብጣት ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኋላ ነበር መጀመሪያ እሱ ከዛ ከ5 ደቂቃ ያህል ዘግይታ እሷ ጡዘት ላይ የደረሱት…፡፡
ከዛ እንደምንም.ተላቀው ወዲህና ወዲያ የነበሩበት ወለል ላይ የተዘረሩት.. ከ7ደቂቃ እረፍት በኋላ እሷ እንደምንም ከተዘረረችበት ተነስታ እየተሳበች ወደሻወር ቤት ሄደች….ውሀውን በላይዋ ላይ ለቀቀች…በሁሉም ነገር በጣም ረክታለች.. የዚህ ወሲባዊ ተራክቦ መሪ እሷ ነበረች.. እርግጥ ያ በግልፅ ለእሱ እንዲሰማው አላደረገችም ቢሆንም እያንዳንዷን ቅንጣት በንቃት አጣጥማታለች፡፡ ከ10 ደቂቃ በኃላ ፎጣዋን አገልድማ ወደመኝታ ቤቱ ስትመለስ ደምሳሽ ጥላው በሄደችበት ወለል ላይ ተዘርሮ እንደተኛ እንቅልፍ ወስዶታል፡፡ እየሳቀች ወደእሱ ቀረበችና በእግሯ ወዘወዘችው..
‹‹ደምሳሽ…እረ ተነስ ሻወር ውሰድና እንተኛ››
‹‹እንዴ... አንቺ ምን አደረግሺኝ?›› እያለ እደምንም ተነሳና ወደ ሻወር ቤት ገባ፡፡
እሷ ሰውነቷን በሎሺን አባበሰችና አልጋ ላይ ወጥታ ከአንገቷ ቀና በማለት ትራስ ተደግፋ ታጥቦ እስኪመጣ በንቃት ትጠብቀው ጀመር….እሱ 5 ደቂቃ አልፈጀበትም፡፡ፎጣውን አገልድሞ ወጣ…
ቁጭ ብላ ሲያያት ‹‹እንዴ ምነው አተኚም እንዴ?››
‹‹ምነው? አንዴ አንደግምም?››አለችው እየሳቀች፡፡
ሰውነቱን የጠቀለለበትን ፎጣ ከላዩ አነሳና የረጠበ ጸገሩን እያደራረቀ‹‹ምነው በቀል ቢሉሽ እንዲህ በአንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ማውደም ነው እንዴ.? ቀስ እያልሽ አይሻልም?››አለና እሱም እንደእሷ አልጋ ላይ ወጣ…ከውስጥ ገብቶ ተኛ፡፡
‹‹ችግር የለም …ዋናው እጅ መስጠትህ ነው››
‹እረ እጅ ሰጥቼያለሁ…በነገራችን ላይ የማሳጅ ችሎታሽ በጣም አስገራሚ ነው የሆነብኝ….ለረጅም አመት በስራው ላይ የቆየሽ እኮ ነው የምትመስይው… በራስሽ ካላበላሸሽው በስተቀር በቀላሉ ውጤታማ እንደምትሆኚ በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ››
‹‹ይሄን ያህል?››
‹‹የምሬን ነው በጣም ነው ያስደመምሺኝ.. ሶስትና አራት አመት በስራው የቆዩ እንኳን ያንቺን ያህል በጥበብ እና በእውቀት አይሰሩም….አንቺ በዚህ ላይ ሶስት አራት ወር ልምድ ካከልሺበት በቃ ልዩ ነው የምትሆኚው፡››
‹‹ለአድናቆትህ በጣም ነው የማመሰግነው..ግን ምነው አድናቆትህ ማሳጁ ላይ ብቻ ሆነ ..ሌላው እስከዚህም ሆነብህ ማለት ነው?፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ አይደል…? በወሲብ ልምዴ እንዲህ አቅሌን ስቼ ስዘረር የመጀመሪያ ገጠመኜ ነው…ብቻ ድንቅ ተማሪ ነሽ.. የመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ስናደርግ..ትኩስ እና ሞቃት ነበርሸ ቢሆንም አብዛኛውን ነገር ለእኔ ነበር አሳልፈሽ የሰጠሸው…ዛሬ ግን እኔ ባሪያሽ ሆኜ ነበር፡፡ በአጠቃላይ በሁሉም ዘርፍ ነው የተቀየርሽው….ምን አልባት ተሰጥኦሽን ይሆናል ያገኘሽው፡፡
‹አንተ እየሰደብከኝ ነው እንዴ…? የታደሉት በስዕል ችሎታቸውና በሙዚቃ ብቃታቸው የተፈጥሮ ታለንታቸውን አገኙ ይባላል…እኔን በወሲብ?፡፡›
ሁሉን ነገር በጥበብና በእውቀት ከከወንሽው አርት ነው…ተሰጥኦ ነው፡፡ እንዴ ትቀለጂያለሽ እንዴ ለአንድ ሴት አርክቶ በእኩል ሰዓት መርካት መቻል እራሱ ድንቅ መሆንን ይጠይቃል፡፡ ብዙ ጊዜ አንዱ አንዱን ለማስደሰት ምን ይህል እንደሚሰቃይ አታውቂም፡፡ ወንድ ልጅ ደግሞ አንዲትን ሴት ሲቀርብ እሷም ሴትነቷን በሚፈልገው መጠን እንዲህ እንደ አንቺ በገለጠችለትና ይበልጥ በእሷ እየተደሰተና እየረካ በሄደ መጠን ነው ቀን ከቀን ይበልጥ በእሷ እየተሳበ እና በአካሏ ብቻ ሳይሆን መላ እሷነቷን እየወደዳትና እየተቀበላት የሚሄደው፡፡
‹‹እሺ ለማንኛውም ነገ ወደ ወሳኙ ተግባራዊ ፈተና የምሰማራበት ቀን ስለሆነ ደክሜ መገኘት አልፈልግም፤ እንተኛ ለዚህ ድንቅ ልብ አቅልጥ አስተያየትህ ግን አልፎ አልፎ ያው እቸገርልሀለሁ›› አለችው፡፡
ተንጠራርቶ መብራቱን እያጠፋ‹‹በነገራችን ላይ የዛሬው አዳራችን ምን አልባት የስንብት ሊሆን ይችላል?››ሲል ነበር ያረዳት፡
የእውነት ከልቧ ደንግጣ ተነስታ ቁጭ አለች‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹ከዚህ በፊት ነግሬሽ የለ…ልጄን ፍለጋ ወደአሜሪካ እንደምሄድ አሁን ፕሮሰሱ ሁሉ.አልቆልኛል...ቪዛም አግኝቼያለሁ….ከአራት ቀን በኋላ እበራለሁ››
‹‹ምን አይነት ጨካኝ ሰው ነህ ግን…? እንዴት አራት ቀን እስኪቀረው ድረስ ሳትነግረኝ?››
‹‹ከባድ ስልጠና ላይ ስለነበርሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም ነበር…››አላት፡፡
‹‹በፈጣሪ…ግን ቶሎ ተመልሰህ ትመጣልህ አይደል?››
‹‹ስለእሱ ምንም የማወራው ነገር የለም….ልጄን ካገኘሁ በኋላ በቀጣይ ባለው ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡››
‹‹ያ ማለት አስከወዲያኛውም ላትመጣ ትችላለህ ማለት ነው?››
ቁዝዝ ብሎ‹‹አዎ ላልመለስ እችላለሁ››አላት፡፡
ተመልሳ ተኛች…እሱም ተኛ…ተቃቅፈው ….እሷ ይሄን የመሰለ መከታ የሆነ ወዳጅ እንዲህ በድንገት እብስ ብሎ ከእጇ ሊያመልጥ መሆኑን ስታውቅ ሆዷን ባር ባር አላት… በጣም ከፋት…ሰሰተችው….ገና ከመሄዱ በፊት ከአሁኑ ናፈቃት... ግን እርቃኑ ከእርቃኗ ተጣብቆ እቅፉ ወስጥ ገብታ ትንፋሿ ሲገርፈው ዝም ብሎ መተኛት አልፈለገም … እሷም በተመሳሳይ… ለሁለተኛ ዙር ፍልሚያ ገቡ፡፡
ጠዋት 12 ሰዓት ነበር ከእንቅልፉ ነቅቶ መኝታውን በመልቀቅ ወደ ኪችን የገባው፤ጥሩ ቁርስ ሰራና አንድ ሰዓት ሲሆን ቀሰቀሳት…ሶስት ሰዓት ስልጠና የምትወስድበት ቪላ ቤት ጋር አድርሷት አንኳኩታ ወደውስጥ ስትገባ…እሱ ወደሌላ ስራው ሄደ፡፡
ስልጠና ቦታዋ ስትደርስ ማንም አልነበረም።ግራ ገባት...አብረዋት የሚሠለጥኑት ተፎካካሪዎቿን ደውላ መጠየቅ አትችልም። ስልክ ቁጥራቸው አልነበራትም። አሰልጣኟ ጋር ደወለች። አይሰራም። ምን ተፈጠረ?"ሰገን ጋር ደወለች። ጎሽ ይጠራል "አለችና ጆሮዋ ላይ ለጠፈች። ዝም ብሎ ይጠራል አይነሳም።
ሊዘጋ ሲል። "ምነው ፈለግሺኝ እዚህ ነኝ" የሚል ድምፅ ከጀርባዋ ሰማች። በፈገግታ ዞር አለች።
"ግቢው ባዶ ሲሆንብኝ ግራ ገብቶኝ ነው"
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ:
….
‹‹ምነው አልክ..?ፒጃማ የለህም እንዴ?››
‹‹አለኝ ግን በማሳጁ ምን ያህል ብቁ ሆነሻል.ስልጠናውስ እንዴት ነበር? የሚለውን ማወቅ እፈልጋለሁ…››
‹‹ተው… እርግጠኛ ነህ?››
‹‹አዎ ምነው ፈራሽ አንዴ.?ነው ወይስ በብቃትሽ አትተማመኝም? እንዳዛ ከሆነ ይቅር፡› ብሎ ፊቱን ወደቁምሳጥኑ መልሶ ሊራመድ ሲል እጁን ለቀም አደረገችውና‹‹መፍራት ያለብህማ አንተ ነህ…ትዝ ይልሀል ያን ቀን ቤትህ አታለህ አስገብተኸኝ የዋህነቴን ተጠቅመህ እዛ የማሳጅ ጠረጴዛ ላይ አስተኝተህ እንዴት እንደተጫወትክብኝ ያንን መበቀል መቻል አለብኝ፡፡›› ብላ እየጎተተች ወደ ማሳጅ ጠረጴዛው ወሰደችና በጀርባው እንዲተኛ አደረገችው፡፡
ከዛ በቅርብ ካለው ቅባት ወደተኮለኮለበት ጠረጴዛ በመሄድ አንዱን መርጣ አነሳችና ጀርባው ላይ አፈሰሰችበትና ከላይ ከጆሮ ግንዱ ጀምራ እስከታች የእግር ጣቶቹ ድረስ በወሰደችው ሰልጠና መሰረት የተለያዩ ቴክኒኮችን በመጠቀመ እያገለባበጠች ለአርባ ደቂቃ ካሸችው በኃላ እጅግ በሚገርም ሰመመንና መመሰጥ ውስጥ ገብቶ ከተዝለፈለፈ በኃላ እንደምንም ከጠረጴዛው ላይ አስነስታ ወለሉ ላይ ዘረረችው…. ከዛማ ቀሚሷን ወደላይ መዥርጣ አውልቃ ከጎኑ ተኛች…ከዛ በኋላ የነበረውን ለማሰብም ይከብዳታል…ያንን ሰፊ የመኝታ ቤት ወለል እየተንከባለሉበት አንዴ የአልጋው ጠርዝ ሲገጫቸው፤አንዴ ከጠረጴዛው እግር ጋር ሲላተሙ አንዴ ስትገለብጠው….ከዛም ሲገለብጣት ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኋላ ነበር መጀመሪያ እሱ ከዛ ከ5 ደቂቃ ያህል ዘግይታ እሷ ጡዘት ላይ የደረሱት…፡፡
ከዛ እንደምንም.ተላቀው ወዲህና ወዲያ የነበሩበት ወለል ላይ የተዘረሩት.. ከ7ደቂቃ እረፍት በኋላ እሷ እንደምንም ከተዘረረችበት ተነስታ እየተሳበች ወደሻወር ቤት ሄደች….ውሀውን በላይዋ ላይ ለቀቀች…በሁሉም ነገር በጣም ረክታለች.. የዚህ ወሲባዊ ተራክቦ መሪ እሷ ነበረች.. እርግጥ ያ በግልፅ ለእሱ እንዲሰማው አላደረገችም ቢሆንም እያንዳንዷን ቅንጣት በንቃት አጣጥማታለች፡፡ ከ10 ደቂቃ በኃላ ፎጣዋን አገልድማ ወደመኝታ ቤቱ ስትመለስ ደምሳሽ ጥላው በሄደችበት ወለል ላይ ተዘርሮ እንደተኛ እንቅልፍ ወስዶታል፡፡ እየሳቀች ወደእሱ ቀረበችና በእግሯ ወዘወዘችው..
‹‹ደምሳሽ…እረ ተነስ ሻወር ውሰድና እንተኛ››
‹‹እንዴ... አንቺ ምን አደረግሺኝ?›› እያለ እደምንም ተነሳና ወደ ሻወር ቤት ገባ፡፡
እሷ ሰውነቷን በሎሺን አባበሰችና አልጋ ላይ ወጥታ ከአንገቷ ቀና በማለት ትራስ ተደግፋ ታጥቦ እስኪመጣ በንቃት ትጠብቀው ጀመር….እሱ 5 ደቂቃ አልፈጀበትም፡፡ፎጣውን አገልድሞ ወጣ…
ቁጭ ብላ ሲያያት ‹‹እንዴ ምነው አተኚም እንዴ?››
‹‹ምነው? አንዴ አንደግምም?››አለችው እየሳቀች፡፡
ሰውነቱን የጠቀለለበትን ፎጣ ከላዩ አነሳና የረጠበ ጸገሩን እያደራረቀ‹‹ምነው በቀል ቢሉሽ እንዲህ በአንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ማውደም ነው እንዴ.? ቀስ እያልሽ አይሻልም?››አለና እሱም እንደእሷ አልጋ ላይ ወጣ…ከውስጥ ገብቶ ተኛ፡፡
‹‹ችግር የለም …ዋናው እጅ መስጠትህ ነው››
‹እረ እጅ ሰጥቼያለሁ…በነገራችን ላይ የማሳጅ ችሎታሽ በጣም አስገራሚ ነው የሆነብኝ….ለረጅም አመት በስራው ላይ የቆየሽ እኮ ነው የምትመስይው… በራስሽ ካላበላሸሽው በስተቀር በቀላሉ ውጤታማ እንደምትሆኚ በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ››
‹‹ይሄን ያህል?››
‹‹የምሬን ነው በጣም ነው ያስደመምሺኝ.. ሶስትና አራት አመት በስራው የቆዩ እንኳን ያንቺን ያህል በጥበብ እና በእውቀት አይሰሩም….አንቺ በዚህ ላይ ሶስት አራት ወር ልምድ ካከልሺበት በቃ ልዩ ነው የምትሆኚው፡››
‹‹ለአድናቆትህ በጣም ነው የማመሰግነው..ግን ምነው አድናቆትህ ማሳጁ ላይ ብቻ ሆነ ..ሌላው እስከዚህም ሆነብህ ማለት ነው?፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ አይደል…? በወሲብ ልምዴ እንዲህ አቅሌን ስቼ ስዘረር የመጀመሪያ ገጠመኜ ነው…ብቻ ድንቅ ተማሪ ነሽ.. የመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ስናደርግ..ትኩስ እና ሞቃት ነበርሸ ቢሆንም አብዛኛውን ነገር ለእኔ ነበር አሳልፈሽ የሰጠሸው…ዛሬ ግን እኔ ባሪያሽ ሆኜ ነበር፡፡ በአጠቃላይ በሁሉም ዘርፍ ነው የተቀየርሽው….ምን አልባት ተሰጥኦሽን ይሆናል ያገኘሽው፡፡
‹አንተ እየሰደብከኝ ነው እንዴ…? የታደሉት በስዕል ችሎታቸውና በሙዚቃ ብቃታቸው የተፈጥሮ ታለንታቸውን አገኙ ይባላል…እኔን በወሲብ?፡፡›
ሁሉን ነገር በጥበብና በእውቀት ከከወንሽው አርት ነው…ተሰጥኦ ነው፡፡ እንዴ ትቀለጂያለሽ እንዴ ለአንድ ሴት አርክቶ በእኩል ሰዓት መርካት መቻል እራሱ ድንቅ መሆንን ይጠይቃል፡፡ ብዙ ጊዜ አንዱ አንዱን ለማስደሰት ምን ይህል እንደሚሰቃይ አታውቂም፡፡ ወንድ ልጅ ደግሞ አንዲትን ሴት ሲቀርብ እሷም ሴትነቷን በሚፈልገው መጠን እንዲህ እንደ አንቺ በገለጠችለትና ይበልጥ በእሷ እየተደሰተና እየረካ በሄደ መጠን ነው ቀን ከቀን ይበልጥ በእሷ እየተሳበ እና በአካሏ ብቻ ሳይሆን መላ እሷነቷን እየወደዳትና እየተቀበላት የሚሄደው፡፡
‹‹እሺ ለማንኛውም ነገ ወደ ወሳኙ ተግባራዊ ፈተና የምሰማራበት ቀን ስለሆነ ደክሜ መገኘት አልፈልግም፤ እንተኛ ለዚህ ድንቅ ልብ አቅልጥ አስተያየትህ ግን አልፎ አልፎ ያው እቸገርልሀለሁ›› አለችው፡፡
ተንጠራርቶ መብራቱን እያጠፋ‹‹በነገራችን ላይ የዛሬው አዳራችን ምን አልባት የስንብት ሊሆን ይችላል?››ሲል ነበር ያረዳት፡
የእውነት ከልቧ ደንግጣ ተነስታ ቁጭ አለች‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹ከዚህ በፊት ነግሬሽ የለ…ልጄን ፍለጋ ወደአሜሪካ እንደምሄድ አሁን ፕሮሰሱ ሁሉ.አልቆልኛል...ቪዛም አግኝቼያለሁ….ከአራት ቀን በኋላ እበራለሁ››
‹‹ምን አይነት ጨካኝ ሰው ነህ ግን…? እንዴት አራት ቀን እስኪቀረው ድረስ ሳትነግረኝ?››
‹‹ከባድ ስልጠና ላይ ስለነበርሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም ነበር…››አላት፡፡
‹‹በፈጣሪ…ግን ቶሎ ተመልሰህ ትመጣልህ አይደል?››
‹‹ስለእሱ ምንም የማወራው ነገር የለም….ልጄን ካገኘሁ በኋላ በቀጣይ ባለው ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡››
‹‹ያ ማለት አስከወዲያኛውም ላትመጣ ትችላለህ ማለት ነው?››
ቁዝዝ ብሎ‹‹አዎ ላልመለስ እችላለሁ››አላት፡፡
ተመልሳ ተኛች…እሱም ተኛ…ተቃቅፈው ….እሷ ይሄን የመሰለ መከታ የሆነ ወዳጅ እንዲህ በድንገት እብስ ብሎ ከእጇ ሊያመልጥ መሆኑን ስታውቅ ሆዷን ባር ባር አላት… በጣም ከፋት…ሰሰተችው….ገና ከመሄዱ በፊት ከአሁኑ ናፈቃት... ግን እርቃኑ ከእርቃኗ ተጣብቆ እቅፉ ወስጥ ገብታ ትንፋሿ ሲገርፈው ዝም ብሎ መተኛት አልፈለገም … እሷም በተመሳሳይ… ለሁለተኛ ዙር ፍልሚያ ገቡ፡፡
ጠዋት 12 ሰዓት ነበር ከእንቅልፉ ነቅቶ መኝታውን በመልቀቅ ወደ ኪችን የገባው፤ጥሩ ቁርስ ሰራና አንድ ሰዓት ሲሆን ቀሰቀሳት…ሶስት ሰዓት ስልጠና የምትወስድበት ቪላ ቤት ጋር አድርሷት አንኳኩታ ወደውስጥ ስትገባ…እሱ ወደሌላ ስራው ሄደ፡፡
ስልጠና ቦታዋ ስትደርስ ማንም አልነበረም።ግራ ገባት...አብረዋት የሚሠለጥኑት ተፎካካሪዎቿን ደውላ መጠየቅ አትችልም። ስልክ ቁጥራቸው አልነበራትም። አሰልጣኟ ጋር ደወለች። አይሰራም። ምን ተፈጠረ?"ሰገን ጋር ደወለች። ጎሽ ይጠራል "አለችና ጆሮዋ ላይ ለጠፈች። ዝም ብሎ ይጠራል አይነሳም።
ሊዘጋ ሲል። "ምነው ፈለግሺኝ እዚህ ነኝ" የሚል ድምፅ ከጀርባዋ ሰማች። በፈገግታ ዞር አለች።
"ግቢው ባዶ ሲሆንብኝ ግራ ገብቶኝ ነው"
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…
‹‹ሄሎ ሶል ምነው?››
‹‹እባክሽ ስለሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር… እኔ ክፍል ድረስ መምጣት ትችያለሽ?››
‹‹መቼ አሁን?››በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ አሁን››
‹‹እሺ በቃ መጣሁ››
‹‹ስልኩን ዘጋና ከተቀመጠበት ተነሳ…መልሶ ቁጭ አለ‹‹ሰለሞን ምን እያደረክ ነው…?በዚህ ሰአት ስለምን ጉዳይነው የምታወራት.?›እራሱን በብስጭት ጠየቀ፡‹‹፡መልሼ ደውዬ በቃ ተይው ነገ ይደርሳል ማለት አለብኝ..››ወሰነና ስልኩን አነሳ….ቁጥሩን ከመጫኑ በፊት የመኝታ ቤቱ በራፍ ተቆረቆረ…..
ስልኩን ወደ አልጋው ወረወረና ተንደርድሮ ሄዶ ከፈተላት…በፀሎት ሮዝ ቀለም ያለው ስስና ልስልስ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች… ፀጉሯን ወደላይ ጠቅልላ በሻሽ አንድ ላይ ጠፍራ አስራዋለች…ውብና መራኪ ሆና ነው እየመጣችው …ወደውስጥ ዘልቃ ገባች‹‹….ምነው በሰላም ነው…?አስደነገጥከኝ እኮ››
ፊት ለፊቷ ተገትሮ ቆመ….ግራ ገባት
‹‹ሶል ምን ሆነሀል…?.ምንድነው የምትነግረኝ?››ጉጉትና ፍራቻ በተቀየጠበት ስሜት ጠየቀችው፡፡
ተንደረደረና በሁለት እጆቹ አገጯን ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ ወደእሱ አስጠጋት… ከንፈሯ ላይ ተጣበቀ….በቀላሉ አለቀቃትም…ምን ይህል ደቂቃ እንደተሳሳሙ ሁለቱም አያቁም …ምን አልባት አንድ ደቂቃ ሊሆን ይችላል …ምን አልባትም ዘላለምም ሊሆን ይችላል….ግን የሁለቱም ልብ በየውስጣቸው ሲንፈራፈር ታውቋቸዋል…ሁለቱም በአየር ላይ የሚንሳፈፉበት ክንፍ እንዳበቀሉ አይነት ስሜት ተሰምቷቸዋል….ለሁለቱም ያልተጠበቀና ልዩ ክስተት ነበር….ሁለቱም ደግሞ ከገዛ ራሳቸው ጋር እንኳን ተነጋግረው ሳይወስኑ በነገሩ መሆን ተስማምተው በደስታ ፈንጥዘዋል፡፡በፀሎት አራት ተኩል ላይ ሰለሞን ክፍል የሄደች ስድስት ሰዓት ሲሆን ነበር ወደክፍሏ የተመለሰችው፡፡እሱንም ለሊሴ ምን ትለኛለች የሚል ይሉኝታ ቀፍድዷት እንጂ እዛው እቅፉ ውስጥ ሟሙታ እየቀለጠች ቢነጋ ደስ ይላት ነበር፡፡እሱም እንደዛው፡፡
በማግስቱ እስከአራት ሰዓት ከአልጋቸው መውረድ አልቻሉም ነበር፡፡
‹‹ልጁ ምን ይለናል ብዬ ነው እንጂ ቀኑን ሙሉ ከዚህ አልጋ ባልወርድ ደስ ይለኝ ነበር››ወ.ሮ ስንዱ ተናገሩ
‹‹ከአልጋው መውረድ ነው ወይስ ከእኔ እቅፍ መውጣት ነው ያስጠላሽ?››
‹‹አንተ ደግሞ…ለምን ታሳፍራኛለህ?››
‹‹ይሄውልሽ ነገ ወደአዲስአበባ እንመለስ የለ ..የልጃችንን የንቅለተከላ የተደረገላትን አመታዊ የመታሰቢያ በአል ድል አድርገን ከደገስን እና አንዳንድ ነገሮችን ካስተካከልን በኃላ..ለአንድ ወር ሲዊዘርላንድ እንሄዳለን፡፡›
‹ማ እና ማ?››
‹‹እኔ እና አንቺ..፡፡ያው አሁን ዳግመኛ እንደተጋባን እና ጉዞውንም ልክ እንደጫጉላ ሽርሽር ቁጠሪው››
‹‹በጣም አጓጓኸኝ ..ግን እኮ ይሄ ያለንበትም ስፍራ ከሲዊዘርላንድ አይተናነስም››
‹‹ገባኝ… ግን ራቅ ብዬ ካንቺ ጋር መጥፋት ነው የምፈልገው…››
‹‹ውይ የፍቅር ግርሻ እኮ መጥፎ ነገር ነው…ግን እንደምታየው ከልጄ ጋር ላለፈው አንድ ወር አልተገናኘሁም…እኔ ለሌላ አንድ ወር ከእሷ ውጭ ማሳለፍ አልችልም››
‹‹አንቺ ደግ…በቃ ይዘናት እንሄዳለን…ሶስታችን እንደቤተሰብ ከእንደገና አብርን በፍቅር እንቆማለት….›
‹‹እሱ ያስማማኛል፡፡››አሉና ከአልጋቸው ላይ ወረዱ…ተጣጥበውና ተዘጋጅተው ከክፍላቸው ሲወጡ አምስት ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡የሰለሞንን ክፍል ሲያንኳኩ አልነበረም…ደወሉለት
..በደቂቃዎች መጣላቸው፡፡
‹‹እንዴት ነበር አዳር?››
‹‹ዕድሜ ላንተ ሁሉ ነገር ውብና ማራኪ ነበር››አቶ ኃይለልኡል መለሱ፡፡
‹‹ጥሩ …አሁን እርግጠኛ ነኝ እርቦችኃላ?››
‹‹አዎ …የራበን ይመስለኛል›››
‹‹በሉ ተከተሉኝ …ቆንጆ ቁርስና ምሳ አንድ ላይ እንዲዘጋጅላችሁ አድርጌለው…››ብሎ ይዟቸው ሄደ..፡፡
በቀይ መንጣፍ ያሸበረቀ ግዙፍ የሞጃ ሳሎን የመሰለ ክፍል ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው….ልክ አዲስ ሙሽሮች እንደሚስተናገዱበት አዳራሽ ውብና ልዩ ተደርጎ ዲኮር ተደርጓል….ግዙፉ ጠረጴዛና ጠረጴዛውን የከበቡት ወንበሮች ከቆዳ የተለበጡ ውብና ልዩ ናቸው…ልዩ ልዩ ባህላዊ ቅርሶች ግድግዳው ሞልተውታል፡፡እየመራ ወሰደና ወንበሩን እየሳበ ሁለቱንም አስቀመጣቸውና ..ከፊት ለፊታቸው ዞሮ ቆመ….
‹‹አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ…ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው፡፡ማለቴ ከአሁን በኃላ ያለውን ቤታችሁ ተመልሳችሁ መደበኛ ስራችሁን እየሰራችሁ የምናከናውነው ይሆናል፡፡እስከአሁን ላለው ግን በእውነት እናንተ ለእኔ ትልቅ ውለታ ስለዋላችሁልኝ ላመሰግናችሁ እወዳለው..ይሄንን ስራ ከልጃችሁ ከበፀሎት ስቀበል በከፍተኛ ፍራቻና በወረደ የራስ መተማመን ነበር…እናንተ ግን ለልጃችሁ ስትሉ ጠንክራችሁ አጠነከራችሁኝ….በሶስት ወርና በአራት ወር እፈተዋላው ያላልኩትን በመሀከላችሁ ያለውን ውስብስብ ችግር በአንድ ወር አዚህ ደረጃ እንዲደርስ አድርጋችሁ አስደመማችሁኝ..ይህ አንድ ወር ለእኔ ታላቅ ትምህርት
ያገኘሁበት ነው..በሀገራችን የማህበራዊ ስሪትና ባህል የጋብቻ አማካሪ ብሎ ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ውጤታማ አይሆንም ተጠቃሚም አይኖርም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ድርጅቴን ልዘጋ እያሰብኩ ባለሁበት ወቅት ነው የእናንተን ስራ ያገኘሁት…አሁን ግን ዘመናዊውን ሳይንስ በሀገራችን ተጫባች ሁኔታ አንፃር ቃኝተን በጥበብ ከተጠቀምነው የብዙ ውስብስብ ጋብቻዎችን ችግር ለመቅረፍ እንደሚቻልና ስራዬም ለማህበረሰቡ ጠቃሚ እንደሆነ እንድረዳ አድርጋችሁኛልና አመሰግናለው….በአጭር ቀናት ውስጥ ባሳያችሁት ውጤት ልጃችሁ ብቻ ሳትሆን እኔም ደስተኛ ነኝ፡፡
‹‹ልጄ ..አንተም እንደምትረዳው ወደእዚህ ጉዳይ ስንገባ ..አንተ ስለምትለው በእኔና ስንዱ መሀከል ስላለው ግንኙነት ማሻሻል ምንም አይነት ፍላጎትም ሆነ እምነት የለኝም ነበር…ልጄን ለማግኘት ስል ነበር ሳልወድ በግዴ የተስማማሁት…እያደረ ግን ሀሳቤን ሙሉ በሙሉ እንድቀይር አድርገሐኛል…ጋብቻዬ ጥሩ ባለመሆኑ ሕይወቴም ምን ያህል የተዛባ እና በጭንቀትና በሀዘን የተሞላ እንደሆነ እንዳስተውል አድርገሐኛል…እኔ ምን የህል አጥቼ ቤተሰቦቼንም ምን ያህል እንዳሳጣኋቸው እንዳስብና ወደቀልቤ እንድመለስ አድርገኀኛል..እኔ ነኝ አንተንም ሆነ ስንዱን ማመስገን አያለብኝ…በእውነት የእድሜ ልክ ባለውለታዬ ነህ…አንተ ከአሁን ወዲያ ልክ እንደልጄ ነህ….በማንኛውም ህይወት ጉዞህ እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ ከጎንህ እንደሆን ልታውቅ ይገባል፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ተነጋ ወዲያ አዲስአበባ እንደተመለስን ልጃችንም ወደቤቷ ትመለሰላች ብዬ ተስፋ አደርጋለው…እሷ ስትመለስ የተቀረውን ነገር እናወራለን፡፡››
ሰለሞን‹‹እሺ ጥሩ አሁን ስለራባችሁ …ከዚህ በላይ በወሬ አልያዛችው ››እጁን ሲያጨበጭብ ነጭ ዩኒፎርም የለበሰ አስተናጋጅ መጣ…..‹‹ምግብ ይቅረብ…መጀመሪያ የእጅ ውሀ አምጡ በላቸው››ሲል አዘዘው…ልጁ በቆመበት በራፍ ላይ ላሉት ልጆች ምልክት ሰጠው፡፡ውብ የሆነ ባህላዊ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ወጣት ሴቶች ውብ የሆነ ወርቅ ቅብ ማስታጠቢያ በእጃቸው ይዘው መጡና….አንደኛዋ አቶ ኃይለልኡልን ሌለኛዋ ወ.ሮ ስንደን ለማስታጠብ ጎንበስ አሉ…ሁለቱም ታጥበው..ቀና ሲሉ በተመሳሳይ ቅፅበት ነው የአንደኛዋ ፊት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…
‹‹ሄሎ ሶል ምነው?››
‹‹እባክሽ ስለሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር… እኔ ክፍል ድረስ መምጣት ትችያለሽ?››
‹‹መቼ አሁን?››በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ አሁን››
‹‹እሺ በቃ መጣሁ››
‹‹ስልኩን ዘጋና ከተቀመጠበት ተነሳ…መልሶ ቁጭ አለ‹‹ሰለሞን ምን እያደረክ ነው…?በዚህ ሰአት ስለምን ጉዳይነው የምታወራት.?›እራሱን በብስጭት ጠየቀ፡‹‹፡መልሼ ደውዬ በቃ ተይው ነገ ይደርሳል ማለት አለብኝ..››ወሰነና ስልኩን አነሳ….ቁጥሩን ከመጫኑ በፊት የመኝታ ቤቱ በራፍ ተቆረቆረ…..
ስልኩን ወደ አልጋው ወረወረና ተንደርድሮ ሄዶ ከፈተላት…በፀሎት ሮዝ ቀለም ያለው ስስና ልስልስ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች… ፀጉሯን ወደላይ ጠቅልላ በሻሽ አንድ ላይ ጠፍራ አስራዋለች…ውብና መራኪ ሆና ነው እየመጣችው …ወደውስጥ ዘልቃ ገባች‹‹….ምነው በሰላም ነው…?አስደነገጥከኝ እኮ››
ፊት ለፊቷ ተገትሮ ቆመ….ግራ ገባት
‹‹ሶል ምን ሆነሀል…?.ምንድነው የምትነግረኝ?››ጉጉትና ፍራቻ በተቀየጠበት ስሜት ጠየቀችው፡፡
ተንደረደረና በሁለት እጆቹ አገጯን ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ ወደእሱ አስጠጋት… ከንፈሯ ላይ ተጣበቀ….በቀላሉ አለቀቃትም…ምን ይህል ደቂቃ እንደተሳሳሙ ሁለቱም አያቁም …ምን አልባት አንድ ደቂቃ ሊሆን ይችላል …ምን አልባትም ዘላለምም ሊሆን ይችላል….ግን የሁለቱም ልብ በየውስጣቸው ሲንፈራፈር ታውቋቸዋል…ሁለቱም በአየር ላይ የሚንሳፈፉበት ክንፍ እንዳበቀሉ አይነት ስሜት ተሰምቷቸዋል….ለሁለቱም ያልተጠበቀና ልዩ ክስተት ነበር….ሁለቱም ደግሞ ከገዛ ራሳቸው ጋር እንኳን ተነጋግረው ሳይወስኑ በነገሩ መሆን ተስማምተው በደስታ ፈንጥዘዋል፡፡በፀሎት አራት ተኩል ላይ ሰለሞን ክፍል የሄደች ስድስት ሰዓት ሲሆን ነበር ወደክፍሏ የተመለሰችው፡፡እሱንም ለሊሴ ምን ትለኛለች የሚል ይሉኝታ ቀፍድዷት እንጂ እዛው እቅፉ ውስጥ ሟሙታ እየቀለጠች ቢነጋ ደስ ይላት ነበር፡፡እሱም እንደዛው፡፡
በማግስቱ እስከአራት ሰዓት ከአልጋቸው መውረድ አልቻሉም ነበር፡፡
‹‹ልጁ ምን ይለናል ብዬ ነው እንጂ ቀኑን ሙሉ ከዚህ አልጋ ባልወርድ ደስ ይለኝ ነበር››ወ.ሮ ስንዱ ተናገሩ
‹‹ከአልጋው መውረድ ነው ወይስ ከእኔ እቅፍ መውጣት ነው ያስጠላሽ?››
‹‹አንተ ደግሞ…ለምን ታሳፍራኛለህ?››
‹‹ይሄውልሽ ነገ ወደአዲስአበባ እንመለስ የለ ..የልጃችንን የንቅለተከላ የተደረገላትን አመታዊ የመታሰቢያ በአል ድል አድርገን ከደገስን እና አንዳንድ ነገሮችን ካስተካከልን በኃላ..ለአንድ ወር ሲዊዘርላንድ እንሄዳለን፡፡›
‹ማ እና ማ?››
‹‹እኔ እና አንቺ..፡፡ያው አሁን ዳግመኛ እንደተጋባን እና ጉዞውንም ልክ እንደጫጉላ ሽርሽር ቁጠሪው››
‹‹በጣም አጓጓኸኝ ..ግን እኮ ይሄ ያለንበትም ስፍራ ከሲዊዘርላንድ አይተናነስም››
‹‹ገባኝ… ግን ራቅ ብዬ ካንቺ ጋር መጥፋት ነው የምፈልገው…››
‹‹ውይ የፍቅር ግርሻ እኮ መጥፎ ነገር ነው…ግን እንደምታየው ከልጄ ጋር ላለፈው አንድ ወር አልተገናኘሁም…እኔ ለሌላ አንድ ወር ከእሷ ውጭ ማሳለፍ አልችልም››
‹‹አንቺ ደግ…በቃ ይዘናት እንሄዳለን…ሶስታችን እንደቤተሰብ ከእንደገና አብርን በፍቅር እንቆማለት….›
‹‹እሱ ያስማማኛል፡፡››አሉና ከአልጋቸው ላይ ወረዱ…ተጣጥበውና ተዘጋጅተው ከክፍላቸው ሲወጡ አምስት ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡የሰለሞንን ክፍል ሲያንኳኩ አልነበረም…ደወሉለት
..በደቂቃዎች መጣላቸው፡፡
‹‹እንዴት ነበር አዳር?››
‹‹ዕድሜ ላንተ ሁሉ ነገር ውብና ማራኪ ነበር››አቶ ኃይለልኡል መለሱ፡፡
‹‹ጥሩ …አሁን እርግጠኛ ነኝ እርቦችኃላ?››
‹‹አዎ …የራበን ይመስለኛል›››
‹‹በሉ ተከተሉኝ …ቆንጆ ቁርስና ምሳ አንድ ላይ እንዲዘጋጅላችሁ አድርጌለው…››ብሎ ይዟቸው ሄደ..፡፡
በቀይ መንጣፍ ያሸበረቀ ግዙፍ የሞጃ ሳሎን የመሰለ ክፍል ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው….ልክ አዲስ ሙሽሮች እንደሚስተናገዱበት አዳራሽ ውብና ልዩ ተደርጎ ዲኮር ተደርጓል….ግዙፉ ጠረጴዛና ጠረጴዛውን የከበቡት ወንበሮች ከቆዳ የተለበጡ ውብና ልዩ ናቸው…ልዩ ልዩ ባህላዊ ቅርሶች ግድግዳው ሞልተውታል፡፡እየመራ ወሰደና ወንበሩን እየሳበ ሁለቱንም አስቀመጣቸውና ..ከፊት ለፊታቸው ዞሮ ቆመ….
‹‹አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ…ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው፡፡ማለቴ ከአሁን በኃላ ያለውን ቤታችሁ ተመልሳችሁ መደበኛ ስራችሁን እየሰራችሁ የምናከናውነው ይሆናል፡፡እስከአሁን ላለው ግን በእውነት እናንተ ለእኔ ትልቅ ውለታ ስለዋላችሁልኝ ላመሰግናችሁ እወዳለው..ይሄንን ስራ ከልጃችሁ ከበፀሎት ስቀበል በከፍተኛ ፍራቻና በወረደ የራስ መተማመን ነበር…እናንተ ግን ለልጃችሁ ስትሉ ጠንክራችሁ አጠነከራችሁኝ….በሶስት ወርና በአራት ወር እፈተዋላው ያላልኩትን በመሀከላችሁ ያለውን ውስብስብ ችግር በአንድ ወር አዚህ ደረጃ እንዲደርስ አድርጋችሁ አስደመማችሁኝ..ይህ አንድ ወር ለእኔ ታላቅ ትምህርት
ያገኘሁበት ነው..በሀገራችን የማህበራዊ ስሪትና ባህል የጋብቻ አማካሪ ብሎ ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ውጤታማ አይሆንም ተጠቃሚም አይኖርም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ድርጅቴን ልዘጋ እያሰብኩ ባለሁበት ወቅት ነው የእናንተን ስራ ያገኘሁት…አሁን ግን ዘመናዊውን ሳይንስ በሀገራችን ተጫባች ሁኔታ አንፃር ቃኝተን በጥበብ ከተጠቀምነው የብዙ ውስብስብ ጋብቻዎችን ችግር ለመቅረፍ እንደሚቻልና ስራዬም ለማህበረሰቡ ጠቃሚ እንደሆነ እንድረዳ አድርጋችሁኛልና አመሰግናለው….በአጭር ቀናት ውስጥ ባሳያችሁት ውጤት ልጃችሁ ብቻ ሳትሆን እኔም ደስተኛ ነኝ፡፡
‹‹ልጄ ..አንተም እንደምትረዳው ወደእዚህ ጉዳይ ስንገባ ..አንተ ስለምትለው በእኔና ስንዱ መሀከል ስላለው ግንኙነት ማሻሻል ምንም አይነት ፍላጎትም ሆነ እምነት የለኝም ነበር…ልጄን ለማግኘት ስል ነበር ሳልወድ በግዴ የተስማማሁት…እያደረ ግን ሀሳቤን ሙሉ በሙሉ እንድቀይር አድርገሐኛል…ጋብቻዬ ጥሩ ባለመሆኑ ሕይወቴም ምን ያህል የተዛባ እና በጭንቀትና በሀዘን የተሞላ እንደሆነ እንዳስተውል አድርገሐኛል…እኔ ምን የህል አጥቼ ቤተሰቦቼንም ምን ያህል እንዳሳጣኋቸው እንዳስብና ወደቀልቤ እንድመለስ አድርገኀኛል..እኔ ነኝ አንተንም ሆነ ስንዱን ማመስገን አያለብኝ…በእውነት የእድሜ ልክ ባለውለታዬ ነህ…አንተ ከአሁን ወዲያ ልክ እንደልጄ ነህ….በማንኛውም ህይወት ጉዞህ እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ ከጎንህ እንደሆን ልታውቅ ይገባል፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ተነጋ ወዲያ አዲስአበባ እንደተመለስን ልጃችንም ወደቤቷ ትመለሰላች ብዬ ተስፋ አደርጋለው…እሷ ስትመለስ የተቀረውን ነገር እናወራለን፡፡››
ሰለሞን‹‹እሺ ጥሩ አሁን ስለራባችሁ …ከዚህ በላይ በወሬ አልያዛችው ››እጁን ሲያጨበጭብ ነጭ ዩኒፎርም የለበሰ አስተናጋጅ መጣ…..‹‹ምግብ ይቅረብ…መጀመሪያ የእጅ ውሀ አምጡ በላቸው››ሲል አዘዘው…ልጁ በቆመበት በራፍ ላይ ላሉት ልጆች ምልክት ሰጠው፡፡ውብ የሆነ ባህላዊ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ወጣት ሴቶች ውብ የሆነ ወርቅ ቅብ ማስታጠቢያ በእጃቸው ይዘው መጡና….አንደኛዋ አቶ ኃይለልኡልን ሌለኛዋ ወ.ሮ ስንደን ለማስታጠብ ጎንበስ አሉ…ሁለቱም ታጥበው..ቀና ሲሉ በተመሳሳይ ቅፅበት ነው የአንደኛዋ ፊት
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
:
:
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
‹‹እሺ ቻው ሁሴን…››ስልኩን ዘጋ፡፡ፈጽሞ ያልጠበቀው ነገር ነው፡፡ድብልቅልቅ የሆነ የሚረብሽ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው፡፡ደስታም መረበሽም ….አሁንም ሶስቱም አንድ ላይ ተገናኝተው ሰሎሜን ከበው ሲቀመጡ ምን እንደሚሰማቸውና ምንስ ሊፈጠር እንደሚችል መገመት አልቻለም፡፡
እርግጥ አሁን እንደድሮው አይደለም ሰሎሜ የአላዛር ህጋዊ ሚስት ሆናለች፡፡ግን ደግሞ በመሀከላቸው ያለው ሸለቆ ስምጥና እሩቅ ነው፡፡እና አላዛር ከበሽታው ማገገም ተስኖት ሁለቱ ከተፋቱ ሰሎሜን መልሶ ለማግኘት ሁለቱ ይፎካከራሉ ማለት ነው…አለማየሁና ሁሴን…..‹‹ምን አልባት እሱ እስካሁን ባለበት ሀገር አንዷን ወዶና አጭቶ ወይንም አግብቶ ሊሆን ይችላል… እንደዛ ከሆነ ግልግል ››ሲል አሰበና እራሱን እንደምንም ለማረጋጋት ጥረት ማድረግ ጀመረ፡፡
የሁሴንን ድምፅ በስልክ ከሰማ በኃላ የአላዛርን የህክምና ውጤት ለማወቅ በጣም ነው የጓጓው…ደውሎ ሊጠይቀው አስበና ደግሞ ምን ብሎ እንደሚጠይቀው ስላልገባው ሀሳቡን ሰረዘ፡፡
…‹‹እራሱን ወይም ልቡን አሞት ቢሆን ኖሮ በቀላሉ ደውዬ የድሮ ጎደኛዬ ልብህን እንዴት ሆንክ ..?አሁን ምን ይሰማሀል…?ምርመራው ምን ውጤት አስገኘ….?ምናምን እያልኩ በዝርዝር እጠይቀው ነበር፡፡››ሲል ተነጫነጨ…ድንገት ብልጭ አለለትና ከተኛበት አልጋ ተነሳና ቁጭ አለ.. ስልኩን ከተቀመጠበት አነሳና ዳታ አበራ…..
ስንፈተ ወሲብ ብሎ ሰርች ሲያደርግ ብዛት ያላቸው መረጃዎች ተዘረገፉለት…የመጀመሪያውን ከፈተ፡፡
ስንፈተ ወሲብ ወይም የወንድ ብልት አለመቆም ችግር ለወንዶች አሳሳቢ ከሆኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው። ይህ ችግር የወንዶችን በራስ መተማመን የሚቀንስና ፍርሃት የሚያሳድር ነው። ስንፈተ ወሲብ ማለት በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የወንድ ልጅ ብልት በደንብ መቆም አለመቻል ነው።
ንባቡን አቆመና ማሰብ ጀመረ..‹‹የእሱ ግን ያለመቆም ችግር ነው እንዴ..?ነው ወይስ ሙሉ በሙሉ ፍላጎት ማጣት…?.››መረጃው ስለሌለው ማሰቡን አቁሞ ንባቡን ቀጠለ፡፡
ስንፈተ ወሲብን ማከም የምንችልባቸው ብዙ መንገዶች አሉ።
• ስኳር የበዛባቸው ምግቦች የወሲብ መነሳሳትን ወይም የወሲብ ፍላጎትን ሊቀንሱ ስለሚችሉ ብዙ ስኳርንና ከፍተኛ ካርቦሀይድሬት ያላቸውን ምግቦች ማስወገድ።
• የኮሌስትሮል መጠናችን ጤነኛ በሚባለው ደረጃ መቆጣጠር።
• የደም ፍሰትን ለመጨመር ከፍተኛ አሚኖ አሲድ ያላችው ምግቦችን መጠቀም።
• በዚንክ የበለፀጉ ምግቦችን መጠቀም እንዲሁም የቴስቴስትሮን ሆርሞን እንዲመረት የሚረዱ ሰፕልመንቶችን መውሰድ።
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት መፍትሄዎች ቀለል ያለ የስንፈተ ወሲብ ችግር ላለባቸው ሰዎች እንደመፍትሄ የተቀመጠ ሲሆን ከዛ ከፍ ያለና አሳሳቢ የሆነ ስንፈተ ወሲብ ችግር ካለብዎ የሜዲካል ህክምና ማግኘት እንደ ኤክስትራኮርፖራል ሾክዌቭ ህክም ማግኘት ይገባል ይላል፡፡የኤክስትራኮርፖራል ሾክዌቭ ህክምና የታካሚው ብልት ውግት አድርጎ በመያዝ ዝቅተኛ ኢንተንሲቲ ባለው ግፊት ሞገድ ወደ 4000 ሾክ በወንዱ ብልት 4 ቦታ ላይ የብልት የደምስሮችን ለማነቃቃት ይሰጣል። በዚህ ህክምና ታካሚው በሳምንት ከ1-2 ጊዜ በተከታታይ ለ12 ሳምንት ህክምናውን መውሰድ አለበት።
የሚያነበው ነገር ሁሉ ምንም እየገባው አይደለም…ልክ ያንቀላፋ ያለን ልብ በኤልኬትሪክ ሾክ መንጭቆ እንደማስነሳት አይነት ህክምና ይሆን እንዴ..?ልክ እንደዛ በብልት ዙሪያ የኤሌክትሪክ ንዝረት በመልቀቅ ተመንጭቆ እንዲነሳና እንዲያቆም ማድረግ ይሆን እንዴ….?ተመንጭቆ ተነስቶ አልተኛም ቢልስ?››በራሱ ጥያቄ እራሱ ሳቀ፡፡
እግዚያብሄር ከዚህ አይነት በሽታ አንዲሰውረው በመፀለይ ስልኩን አጠፋና መልሶ ተኛ፡፡
በሶስተኛው ቀን ከስራ ወደቤት እየተመለሰ መንገድ ላይ እያለ አላዛር ደወለለት፡፡
‹‹ሄሎ አላዛር እንዴት ነህ?››
‹‹ምንም አልል ሰላም ነኝ››
ምን ሊነግረው እንደደወለለት ለማወቅ በከፍተኛ ጉጉት ‹‹አይ ጥሩ ነው…ምነው ፈለከኝ….?.››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹አዎ …ነገ ማታ እራት ብጋብዝህ ብዬ አሰብኩ››
‹‹ይቻላል….የትና በስንት ሰዓት እንደምንገኛኝ ንገረኝ..እገኛለሁ››
‹‹ጥሩ …ቴክስት አደርግልሀለው››
‹‹እሺ እጠብቃለሁ….ግን ሰላም ነው አይደል…?ማለቴ የተነጋገርነው ህክምና በተመለከተ አዲስ ነገር አለ?››በመከራና በጭንቀት ጥያቄውን አፈረጠው…
እስከነገ እንዴት ብሎ አምቆ ይያዘው…?‹‹የእራት ግብዣው ሙሉ በሙሉ ተፈወስኩ ብሎ የምስራች ሊለኝ ቢሆንስ?.››ሲል አሰበና ተጨነቀ፡፡ የእሱ የምስራች ማለት ለእሱ በተዘዋወሪ መርዶ ነው….
‹‹አሌክስ ያው በተነጋገርነው መሰረት ቀናቶች አሉኝ አይደል?››
‹‹አዎ ..20 ቀን አለህ…እንዲሁ ሂደቱ እንዴት እየሄደልህ ነው የሚለውን ለማወቅ ነው››
‹‹ለጊዜው ሁሉ ነገር በሂደት ላይ ስላለ መጨራሻውን በእርግጠኝነት አላውቅም ..ሀኪሞቹም የሚያውቁ አይመስለኝም››
‹‹ጥሩ ..በእኔ በኩል ላግዝህ የምትፈልገው ነገር ካለ ሁሉ ጊዜ አለሁልህ…አሁን መራራቃችንን ሳይሆን የልጅነት ቅርበታችንን አስበህ ምንም ነገር ልትጠይቀኝ ትችላለህ….ይሄ ነገር ተስተካክሎ ሁለት የልጅነት ጓደኞቼ ደስተኛ የሆነ ትዳራቸውን እንዲያስቀጥሉ እፈልጋለው…ሁለታችሁንም ስል ማድረግ ያለብኝን ሁሉ አደርጋለሁ››አለው…ንግግሩ ለራሱ ጆሮ እንግዳ ስሜት ነው የፈጠረበት፡፡
‹‹በእውነት አሌክስ ይህንን መስማቴ ደስ ብሎኛል…በቀደም ቢሮህ ተገናኝተን በጉዳዩ ላይ ስንወያይ ንግግርህ ጨከን ያለ ነበር…ይቅርታ አድርግልኝና እንደውም…የሄ ልጅ የእኛን መለያየት ይፈልጋል እንዴ?ብዬ እንዳስብ ነበር ያደረከኝ..ያንን ስሜቴን ደግሞ በእለቱ ነግሬሀለው››ሲል እውነቱን አፍርጦ ነገረው፡፡
እንደዛ ሲለው ዛሬም መደንገጡ አልቀረም….ያን ያህል እስከሚያስታውቅበት እንደዘባረቀ አልተሰማውም ነበር…..ማስተባበሉን ቀጠለ‹‹እንዴ ምን ነካህ ?ለምንድነው እንድትለያዩ የምፈልገው?››
‹‹ያው ታውቃለህ አይደል…..?››
‹‹ምኑን ነው የማውቀው?››
‹‹ያው ልጅ ሆነን ጀምሮ ሶስታችንም ነበር የምናፈቅራት››
‹‹ልጅ ሆነን ነበራ ››
‹‹አሁን እንደውም በይበልጥ ውብና ማራኪ ሆናለች እኮ…እንደውም በበለጠ በፍቅር የምታማልለው አሁን ነው…ማለቴ ስሜቱን በራሴ አውቀዋለው..በየጊዜው ትንሽ ባደገችና እድሜ በጨመረች ቁጥር ውብና ማሪኪ እየሆነች እኔም አምርሬ እያፈቀርኳት ነው እየሄድኩ ያለሁት››
‹‹አላአዛር…አንተ እኮ እንደዛ ቢሰማህ ሚስትህ ስለሆነች ነው…..እኛን በተመለከተ የምታወራው ግን የልጅነትና ያለፈ ታሪክ ነው››
‹‹ለማንኛውም እንደዛ ስላሰብኩህ ይቅርታ…በእውነት ያንተን እገዛና ማበረታቻ በጣም ነው የሚያስፈልገኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ ከአንተ በተሻለ የሚረዳኝና የሚያግዘኝ ሰው እደሌለ እኔም አምናለው››
‹‹አዎ እንደዛ ጥሩ ነው..በል አሁን ቻው …ነገ እንገናኛለን፡፡››
‹‹.ቻው እሺ ..አመሰግናለሁ፡፡››
:
:
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
‹‹እሺ ቻው ሁሴን…››ስልኩን ዘጋ፡፡ፈጽሞ ያልጠበቀው ነገር ነው፡፡ድብልቅልቅ የሆነ የሚረብሽ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው፡፡ደስታም መረበሽም ….አሁንም ሶስቱም አንድ ላይ ተገናኝተው ሰሎሜን ከበው ሲቀመጡ ምን እንደሚሰማቸውና ምንስ ሊፈጠር እንደሚችል መገመት አልቻለም፡፡
እርግጥ አሁን እንደድሮው አይደለም ሰሎሜ የአላዛር ህጋዊ ሚስት ሆናለች፡፡ግን ደግሞ በመሀከላቸው ያለው ሸለቆ ስምጥና እሩቅ ነው፡፡እና አላዛር ከበሽታው ማገገም ተስኖት ሁለቱ ከተፋቱ ሰሎሜን መልሶ ለማግኘት ሁለቱ ይፎካከራሉ ማለት ነው…አለማየሁና ሁሴን…..‹‹ምን አልባት እሱ እስካሁን ባለበት ሀገር አንዷን ወዶና አጭቶ ወይንም አግብቶ ሊሆን ይችላል… እንደዛ ከሆነ ግልግል ››ሲል አሰበና እራሱን እንደምንም ለማረጋጋት ጥረት ማድረግ ጀመረ፡፡
የሁሴንን ድምፅ በስልክ ከሰማ በኃላ የአላዛርን የህክምና ውጤት ለማወቅ በጣም ነው የጓጓው…ደውሎ ሊጠይቀው አስበና ደግሞ ምን ብሎ እንደሚጠይቀው ስላልገባው ሀሳቡን ሰረዘ፡፡
…‹‹እራሱን ወይም ልቡን አሞት ቢሆን ኖሮ በቀላሉ ደውዬ የድሮ ጎደኛዬ ልብህን እንዴት ሆንክ ..?አሁን ምን ይሰማሀል…?ምርመራው ምን ውጤት አስገኘ….?ምናምን እያልኩ በዝርዝር እጠይቀው ነበር፡፡››ሲል ተነጫነጨ…ድንገት ብልጭ አለለትና ከተኛበት አልጋ ተነሳና ቁጭ አለ.. ስልኩን ከተቀመጠበት አነሳና ዳታ አበራ…..
ስንፈተ ወሲብ ብሎ ሰርች ሲያደርግ ብዛት ያላቸው መረጃዎች ተዘረገፉለት…የመጀመሪያውን ከፈተ፡፡
ስንፈተ ወሲብ ወይም የወንድ ብልት አለመቆም ችግር ለወንዶች አሳሳቢ ከሆኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው። ይህ ችግር የወንዶችን በራስ መተማመን የሚቀንስና ፍርሃት የሚያሳድር ነው። ስንፈተ ወሲብ ማለት በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የወንድ ልጅ ብልት በደንብ መቆም አለመቻል ነው።
ንባቡን አቆመና ማሰብ ጀመረ..‹‹የእሱ ግን ያለመቆም ችግር ነው እንዴ..?ነው ወይስ ሙሉ በሙሉ ፍላጎት ማጣት…?.››መረጃው ስለሌለው ማሰቡን አቁሞ ንባቡን ቀጠለ፡፡
ስንፈተ ወሲብን ማከም የምንችልባቸው ብዙ መንገዶች አሉ።
• ስኳር የበዛባቸው ምግቦች የወሲብ መነሳሳትን ወይም የወሲብ ፍላጎትን ሊቀንሱ ስለሚችሉ ብዙ ስኳርንና ከፍተኛ ካርቦሀይድሬት ያላቸውን ምግቦች ማስወገድ።
• የኮሌስትሮል መጠናችን ጤነኛ በሚባለው ደረጃ መቆጣጠር።
• የደም ፍሰትን ለመጨመር ከፍተኛ አሚኖ አሲድ ያላችው ምግቦችን መጠቀም።
• በዚንክ የበለፀጉ ምግቦችን መጠቀም እንዲሁም የቴስቴስትሮን ሆርሞን እንዲመረት የሚረዱ ሰፕልመንቶችን መውሰድ።
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት መፍትሄዎች ቀለል ያለ የስንፈተ ወሲብ ችግር ላለባቸው ሰዎች እንደመፍትሄ የተቀመጠ ሲሆን ከዛ ከፍ ያለና አሳሳቢ የሆነ ስንፈተ ወሲብ ችግር ካለብዎ የሜዲካል ህክምና ማግኘት እንደ ኤክስትራኮርፖራል ሾክዌቭ ህክም ማግኘት ይገባል ይላል፡፡የኤክስትራኮርፖራል ሾክዌቭ ህክምና የታካሚው ብልት ውግት አድርጎ በመያዝ ዝቅተኛ ኢንተንሲቲ ባለው ግፊት ሞገድ ወደ 4000 ሾክ በወንዱ ብልት 4 ቦታ ላይ የብልት የደምስሮችን ለማነቃቃት ይሰጣል። በዚህ ህክምና ታካሚው በሳምንት ከ1-2 ጊዜ በተከታታይ ለ12 ሳምንት ህክምናውን መውሰድ አለበት።
የሚያነበው ነገር ሁሉ ምንም እየገባው አይደለም…ልክ ያንቀላፋ ያለን ልብ በኤልኬትሪክ ሾክ መንጭቆ እንደማስነሳት አይነት ህክምና ይሆን እንዴ..?ልክ እንደዛ በብልት ዙሪያ የኤሌክትሪክ ንዝረት በመልቀቅ ተመንጭቆ እንዲነሳና እንዲያቆም ማድረግ ይሆን እንዴ….?ተመንጭቆ ተነስቶ አልተኛም ቢልስ?››በራሱ ጥያቄ እራሱ ሳቀ፡፡
እግዚያብሄር ከዚህ አይነት በሽታ አንዲሰውረው በመፀለይ ስልኩን አጠፋና መልሶ ተኛ፡፡
በሶስተኛው ቀን ከስራ ወደቤት እየተመለሰ መንገድ ላይ እያለ አላዛር ደወለለት፡፡
‹‹ሄሎ አላዛር እንዴት ነህ?››
‹‹ምንም አልል ሰላም ነኝ››
ምን ሊነግረው እንደደወለለት ለማወቅ በከፍተኛ ጉጉት ‹‹አይ ጥሩ ነው…ምነው ፈለከኝ….?.››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹አዎ …ነገ ማታ እራት ብጋብዝህ ብዬ አሰብኩ››
‹‹ይቻላል….የትና በስንት ሰዓት እንደምንገኛኝ ንገረኝ..እገኛለሁ››
‹‹ጥሩ …ቴክስት አደርግልሀለው››
‹‹እሺ እጠብቃለሁ….ግን ሰላም ነው አይደል…?ማለቴ የተነጋገርነው ህክምና በተመለከተ አዲስ ነገር አለ?››በመከራና በጭንቀት ጥያቄውን አፈረጠው…
እስከነገ እንዴት ብሎ አምቆ ይያዘው…?‹‹የእራት ግብዣው ሙሉ በሙሉ ተፈወስኩ ብሎ የምስራች ሊለኝ ቢሆንስ?.››ሲል አሰበና ተጨነቀ፡፡ የእሱ የምስራች ማለት ለእሱ በተዘዋወሪ መርዶ ነው….
‹‹አሌክስ ያው በተነጋገርነው መሰረት ቀናቶች አሉኝ አይደል?››
‹‹አዎ ..20 ቀን አለህ…እንዲሁ ሂደቱ እንዴት እየሄደልህ ነው የሚለውን ለማወቅ ነው››
‹‹ለጊዜው ሁሉ ነገር በሂደት ላይ ስላለ መጨራሻውን በእርግጠኝነት አላውቅም ..ሀኪሞቹም የሚያውቁ አይመስለኝም››
‹‹ጥሩ ..በእኔ በኩል ላግዝህ የምትፈልገው ነገር ካለ ሁሉ ጊዜ አለሁልህ…አሁን መራራቃችንን ሳይሆን የልጅነት ቅርበታችንን አስበህ ምንም ነገር ልትጠይቀኝ ትችላለህ….ይሄ ነገር ተስተካክሎ ሁለት የልጅነት ጓደኞቼ ደስተኛ የሆነ ትዳራቸውን እንዲያስቀጥሉ እፈልጋለው…ሁለታችሁንም ስል ማድረግ ያለብኝን ሁሉ አደርጋለሁ››አለው…ንግግሩ ለራሱ ጆሮ እንግዳ ስሜት ነው የፈጠረበት፡፡
‹‹በእውነት አሌክስ ይህንን መስማቴ ደስ ብሎኛል…በቀደም ቢሮህ ተገናኝተን በጉዳዩ ላይ ስንወያይ ንግግርህ ጨከን ያለ ነበር…ይቅርታ አድርግልኝና እንደውም…የሄ ልጅ የእኛን መለያየት ይፈልጋል እንዴ?ብዬ እንዳስብ ነበር ያደረከኝ..ያንን ስሜቴን ደግሞ በእለቱ ነግሬሀለው››ሲል እውነቱን አፍርጦ ነገረው፡፡
እንደዛ ሲለው ዛሬም መደንገጡ አልቀረም….ያን ያህል እስከሚያስታውቅበት እንደዘባረቀ አልተሰማውም ነበር…..ማስተባበሉን ቀጠለ‹‹እንዴ ምን ነካህ ?ለምንድነው እንድትለያዩ የምፈልገው?››
‹‹ያው ታውቃለህ አይደል…..?››
‹‹ምኑን ነው የማውቀው?››
‹‹ያው ልጅ ሆነን ጀምሮ ሶስታችንም ነበር የምናፈቅራት››
‹‹ልጅ ሆነን ነበራ ››
‹‹አሁን እንደውም በይበልጥ ውብና ማራኪ ሆናለች እኮ…እንደውም በበለጠ በፍቅር የምታማልለው አሁን ነው…ማለቴ ስሜቱን በራሴ አውቀዋለው..በየጊዜው ትንሽ ባደገችና እድሜ በጨመረች ቁጥር ውብና ማሪኪ እየሆነች እኔም አምርሬ እያፈቀርኳት ነው እየሄድኩ ያለሁት››
‹‹አላአዛር…አንተ እኮ እንደዛ ቢሰማህ ሚስትህ ስለሆነች ነው…..እኛን በተመለከተ የምታወራው ግን የልጅነትና ያለፈ ታሪክ ነው››
‹‹ለማንኛውም እንደዛ ስላሰብኩህ ይቅርታ…በእውነት ያንተን እገዛና ማበረታቻ በጣም ነው የሚያስፈልገኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ ከአንተ በተሻለ የሚረዳኝና የሚያግዘኝ ሰው እደሌለ እኔም አምናለው››
‹‹አዎ እንደዛ ጥሩ ነው..በል አሁን ቻው …ነገ እንገናኛለን፡፡››
‹‹.ቻው እሺ ..አመሰግናለሁ፡፡››