ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
የአገራችን ቅዱሳን እውን መንፈሳዊ ናቸው ?? #በአገራችን ቅዱሳን ተብለው ታቦት ተቀርጾ -ቀን ተሰይሞ -ገድል ተጽፎላቸው ቃል ኪዳን ተቀብለዋል እየተባሉ ከወር እስከወር የሰው ልብ ላይ ነግሰው የአምላክ ገንዘብ የሆነውን ስግደትና ዝማሬ መስዋእትም በጸጋ ስም የሚኮመኩሙ የቡልጋ የትግራይና የጎጃም ተወላጅ የሆኑ አፈጣጠራቸው አኑዋኑዋራቸውና ትምህርታቸው አለም ከተፈጠረ ጀምሮ ያልተሰማ #ክንፍ…


ቅዱስ እውነት ???

#ገድለ ተክለሃይማኖት፥ 48:1- 4

" አንድ ቀን በባሕር ዳር ተቀምጦ ሳለ፥ ሰይጣን ከባሕሩ ወጣ። የአባታችንንም ደቀመዝሙር ያዘው። አንተ ርኩስ መንፈስ ከልጄ ውጣ እያለ በመስቀል ምልክት አማተበ። ሰይጣኑም ዛሩም ደቀመዝሙሩን ትቶ ፈጥኖ ሸሸ። ሊያመልጥም ወደደ። ብፁዕ አባታችንም አማተበበት። ወደ ባሕሩ ሊገባ ባይቻለው በጥልቁ ባሕር ወደብ ቆመ። ብፁዕ አባታችንም ሄዶ #በእጁ #ያዘው። ያን ጊዜ ዕጡ ወደቀና ኃይሉም ደከመና ለሁሉም በግልጥ ታየ።
“...ስምህ ማን ነው?” አለው።
"ባሕረ አልቅም።"
"እንግዲህ #ከእኔ ጋር #ትሄዳለህን ወይስ ወደ ማደሪያህ #ትመለሳለህ?” አለ።
"ከእንግዲህ ወዲህ ወደ ማደሪያዬ መመለስ አይቻለኝም። #በማማተብህ ስልጣኔን ሽረኸዋልና።" አለው።
አባታችን ተክለሃይማኖትም ወስዶ #ገረዘው፥ ወደ ፍፁም #ክርስቲያንነትም ለወጠው። ስሙንም #ክርስቶስ ኃረዮ ማለትም #ክርስቶስ የመረጠው ብሎ ጠራው። ብፁዕ አባታችንን ሲያገለግለው ኖረ። ከጥቂትም ቀን በኋላም የምንኩስናውን ልብስ አልብሶ ወደ ባዕቱ አገባው። ይህችውም ደብረ አሰቦ ናት። ሰይጣን #ሞቶ #መንግስተ ሰማያት እስኪገባ ድረስ በተረፈው ዘመኑ ሁሉ #መነኮሳትን #ደስ #የሚያሰኝ#እግዚአብሔርንም #የሚወድ ሆነ።
********

በኦርቶዶክስ ቤተ እምነት ውስጥ ያሉ #ድርሳናት#ገድላት#ሰይፈ ሥላሴ፥ #ክርስቶስ ሳምራ፥ #ገድለ ክርስቶስ፥ #ተዓምረ ማርያም፥ #መልክዓ መላዕክታት፥ #ውዳሴ ማርያም እንዲሁም በስድሳ ስድስቱ የመጽሐፍ ቅዱስ መፃሕፍት ላይ #የተጨመሩ ሌሎች መፅሐፍት መፅሐፍ ቅዱስን እጅግ የሚፃረሩ #ፀረ ክርስቶስ፣ #የደብተራ ሥጋዊና አጋንንታዊ ውጤት ናቸው።
#አጋንንት ሳቢ #ደብተራዎች የጻፉት የረከሱ ገድላት መካከል #ገድለ ተክለሃይማኖት አንዱ ነው።

እስከ መቼ ጌታ እግዚአብሔርን ነው የማመልከው እያልክ #በተክለሃይማኖት ስም የአጋንንትን ጽዋ ትጠጣለህ። እርም ባለበት መርገም አይርቅም። ልብህን ወደ እውነተኛው #የእግዚአብሔር ቃል ወደ #መፅሐፍ ቅዱስ እና ወደ ነፍስህ አዳኝ ወደ #ጌታ እየሱስ ክርስቶስ ለፍሬ በሆነ ንስሐ ተመልስ።
********

"እሁድና ሐሙስ እባብ የገደለ የክርስቲያን ወገን ሁሉ ኃጢያቱ ይሰረይለታል፤ ብለህ ለልጆችህ ንገራቸው።" ብሎ ጌታዬ እየሱስ ክርስቶስ የነገረኝን አሁንም እነግራችኋለሁ። በልባችሁ ጠብቁት።
#ገድለተክለሃይማኖት፥51፥6
********
🕇 የከበረውን የሕያው እግዚአብሔርን ቅዱስ ቃል #መፅሐፍ ቅዱስን ገለባ ከሆነውና ከረከሰው ስጋዊና አጋንንታዊ መልዕክት ጋር ምን አንድ አደረገው???
#ሰይጣንን ይዤ #ገረዝኩት#አጠመኩት#ቅስና አስተምሬ #የኦርቶዶክስ #መነኩሳትን #አገልግሎ #ሰይጣን ወደ #መንግስተ ሰማያት ገብቶዋል ብሎ እራሱ በፃፈው በገድለ ተክለሃይማኖት.48:1-4 ላይ መስክሯል።
********
#ገድለ ተክለሃይማኖት፥ 48:1- 4 :- አንድ ቀን በባሕር ዳር ተቀምጦ ሳለ፥ ሰይጣን ከባሕሩ ወጣ። ......
********
ይህ የአጋንንት ጎታቾች ክፉ ግብር እንጂ የእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ጨርሶ አይደለም። #ሰይጣን መንግስተ ሰማያት ገብቶማ ቢሆን ኖሮ ምድር የንፁሐንና የጻድቃን ደም ባልፈሰሰባት ነበር። ዋይታና ልቅሶ፥ ረሃብና ጥማት፥ ጦርነትና ሞት ባልተገኘባት ነበር።
የተረገመው ሰይጣን ግን ኦርቶዶክስ እንደምትከተለው የተክለ ሃይማኖት የሐሰት ትምህርት በመንግሥተ ሰማያት ሳይሆን በምድርና በአየር በጥልቁም ሆኖ የአመፅ፥ የክፋት፥ የጭካኔ፥ የእርኩስት፥ የማታለልና የሐሰት ክፉ ጨካኝ ደም አፍሳሽ ስራውን በምድር ሁሉ ላይ እያደረገ ነው።
ለሰይጣን መንግስተ ሰማያት ቦታ እንደሌለ አላነበቡም ይሆን..👇

የማቴዎስ ወንጌል 25:41

በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል። እናንተ ርጉማን፥ #ለሰይጣንና ለመላእክቱ #ወደ #ተዘጋጀ ወደ #ዘላለም #እሳት ከእኔ ሂዱ።

ከዚህ በላይ #ለሰይጣን #ጠበቃና #አገልጋይ ማን ነው?
ከዚህ በላይ ምን #የተረገመና እርም ምን አለ?
ከዚህ በላይ #መናፍቅ ማን ነው?
ከዚህ በላይ #ፀረ ክርስቶስ ማን ነው?

ኦርቶዶክስ #ገድላትን#ድርሳናትን#ውዳሴያትን#መልክዓ #መላዕክትንና#ሰይፈ ሥላሴ፥ #ክርስቶስ ሳምራ፥ #ገድለ ክርስቶስ፥ #ተዓምረ ማርያም፥ ሌሎችንም #ፀረ #ክርስቶስ መጻሕፍቶቿን አቃጥላና ጥላ ልብን በትህትና በማድረግ መጽሐፍ ቅዱስን ብቻ በመከተል ተሐድሶ ማድረጓ በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ የእምነት ተከታዮቿ የዘላለም ሕይወትና ክብር ነው። ልብን እልከኛ ማድረግ ግን ጌታ እየሱስ ክርስቶስን እንደሰቀሉት ለአይሁድ ፈሪሳውያኖችም አልሆነም።

@gedlatnadersanat
👇👇
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
ተአምረ ማርያም እርግማን እንጂ በረከት የሌለው መጽሐፍ ብዙዎች ተአምረ ማርያም ቅዱስ መጽሐፍ እንደሆነ፣ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት እንደተጻፈ ይናገራሉ። እነርሱ እንደሚሉት ከሆነና የእግዚአብሔር እስትንፋስ ከሆነ እንደ ቅዱሱ መጽሐፍ ፍቅር ፍቅር የሚሸት፣ የእግዚአብሔር ምህረት የሚታይበት መጽሐፍ መሆን አለበት። ነገር ግን መጽሐፉ ከዚህ ተቃራኒ እንደሆነ እስካሁንም ብዙ እያየን መተናል የሚከተሉት ሃሳቦችም…


#ተአምረ ማርያም የተባለው ጉደኛ መጽሐፍ የምንወዳትን ድንግል ማርያምን ያከበረ የሚመስል ነገር ግን #ስድብ እና #ክህደት የሞላበት ስለመሆኑ እርግጥ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ከተጻፈ #ከ1400 ዓመት በኋላ በኢትዮጵያ ንጉሥ በዘርዓ ያዕቆብ የተደረሰ ሲሆን በወቅቱ የነበሩ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት እና ምእመናን ይህ ልዩ ወንጌል ከሐዋርያት ትምህርት የወጣ ስለሆነ #አንቀበለውም በማለታቸው፣ እስከ #አንገታቸው በጉድጓድ #ተቀብረው #በጭንቅላታቸው ላይ #የፈረስና #የከብት #መንጋ #እንደተነዳባቸው ምላሳቸውንና አፍንጫቸውን #እንደተቆረጡ በሚገርም ሁኔታ ራሱ #ተአምረ ማርያም ይመሰክራል።
( #ታምር 24 እና 25 ገጽ 112- 121።)
*****************************
***

አብዛኛው የቤተክርስቲያናችን የዋህ ምዕመን እምነቱን የመሠረተ የሚመስለው #በታምረ ማርያም ላይ ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ እንኳ #ታምሯን #ሰምተን እንምጣ እንጂ ወንጌል #ተምረን አንምጣ ብለው አያስቡም አይናገሩም። በተለይ እሁድ እሁድ ታምር የሚያነብ እንጂ ወንጌል ለማስተማር የሚያስብ ቄስም የለንም።
#ከ400,000 ካህናት በላይ እንዳላት የሚነገርላት ቤተ ክርስቲያናችን #ታምረ ማርያም አንብቦ ከማሳለም ያላፈ አገልግሎት የሚሰጥበት አይደለም። በጣም በሚገርም ሁኔታ #ታምሯን #ሰምቶ የሄደ #ሥጋውና #ደሙን #እንደተቀበለ #ይቆጠርለታል የሚለው ባዕድ ወንጌል ስለ ጌታ ራት ከተሰጡት የስህተት ትምህርቶች ውስጥ በዋንኛነት ከሚጠቀሱት #አንዱ ነው።
አረ እንደው በፈጠራቹ ህሊና ያለው ሰው አሁን ይሄን ምን ይላል?
ክርስቲያን የሆነ ሰው አላልኩም
እንደው ህሊና ብቻ ያለው ሰው።

#ብዙ ጊዜ ደግሞ ስህተቱን እያወቁ በዝምታ የሚያልፉ አገልጋዮች አጋጥመውኛል ለምን እውነቱን እንደማይናገሩ ስጠይቅ ለዚህ ጊዜዬን አላጠፋም ወንጌል ሲረዱ እውነቱ ይገለጥላቸዋል የሚል ነው። እንደ እውነቱ ካየነው #የወንጌል #ብርሃን የማይፈታው ጨለማ የለም እንዲሁም ወንጌል ላይ ትኩረት ማድረጉም እደግፈዋለው ነገር አንድ የማልስማማበት ነገር አለ ስንቱን ወደ ዘላለማዊ ሞት እየነዳ ያለውን ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ይልቅ #የተአምረ ማርያም ዓይነቱ ስጋ ስጋ የሚሸቱ የሰይጣን ሀሳብና ምክሩ የሰፈረበትን በግልፅ መዝለፍ ተገቢ ነው ብዬ አስባለው። ቃሉም እንደዛ ነውና የሚለው
የይሁዳ መልእክት 1:22

አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ፥ አንዳንዶችንም #ከእሳት #ነጥቃችሁ አድኑ፥

#ብዙ ሰዎች ይሰድቡኛል ለምን ራስህን አትመለከትም ምናምን እኔ ግን አሁንም ቢሆን በሰው ልብ ውስጥ የነገሰውን በብልሃት የተፈጠረን #ተረትና #መንፈሳዊ #ይዘት ባለው ነገር የሚሰራውን #ክፉ ወገኖቼ ላይ እንዳይሰለጥን የበኩሌን አደርጋለው። የገድላትንም ደባ ባለኝ መረዳትና እግዚአብሔር በሰጠኝ #ፀጋ እጋደላለው በቃ ይሄ ነው የእኔ #አቋም
የገድላትን ደባ በማጋለጥ ሂደት ውስጥ ብዙ ሰዎች መልካም የሆነውን #እውነት ለይተውበታል ለዚህም በውስጥ መስመር የሚደርሰኝ አበረታች ቃላት ወደ ፊት እንድገፋበት ብርታት ሆኖኛል። እናም አጋልጣለው የሚሰማ ባይኖር እንኳ አልተውም። በእርግጥ #ከእውነቱም መሸሽ አይቻልም።

ብቻ ግን ለዛሬ ከላይ በርዕሱ እንደጠቀስኩት #የተአምረ ማርያምን ደባ #ከበለዔ #ሰብ ጋራ ያለውን ታሪክ በተያያዘ የኑሮአችን የመኖሪያ ልክ ወይም ቱንቢ በሆነው በሕያውና በሚሰራው #በቅዱሱ #የእግዚአብሔር #ቃል እንፃር እንመለከታለን መልካም #ንባብ
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ብዙ ሴቶች #ማርያም በሚል ስም ይጠራሉ[1]። [ለምሳሌ]👇 〽️ 1፦ "የሙሴ እህት ማርያም" /ዘጸ 2፥4-8/ ▶️ የዚችን #ማርያም ታሪክ #በመጽሀፍቅዱስ ውስጥ ስናይ #ወንድሟ #ሙሴ በወንዝ #ዳር #በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን #ለማወቅ ስትመለከት ወደ ወንዙ የመጣችውን #የፈርኦንን #ልጅ #በጥበብ አነጋግራና #እንድታጠባው የገዛ #እናታቸውን #በሞግዚትነት ስም አገናኝታ…
▶️ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ለ"ማርያም" ለሚለው ስም የተሰጡ #ትርጉሞች #የቤተስክርስቲያን #አባቶችም ሆኑ #ወጣት #ሰባኪያንና #ህዝቡም በብዛት የሚያውቁት #የተለመደ #ትርጉም ነው። የሚገርመው ደሞ #የስሙ #ትርጉሞች ብዙ #ማርያም የተባሉ #ሴቶች እያሉ ማእከል ያደረገው ግን #የጌታችን #እናት #ድንግል #ማርያምን ብቻ ይመስላል። እነዚን #ትርጉሞች ይዘን ለሌሎች < #ማርያም> ለተባሉ #ሴቶች ትርጉሙን ብንሰጣቸው #የትርጉሙ #ባለቤቶች ራሱ #ይሸማቀቁበታል። [ለምሳሌ]፦
#በስም #ደረጃ ከክርስቶስ እናት ጋር #ምንም #ልዩነት ላልነበራት #ለመግደላዊት #ማርያም ትርጓሜውን ብንሰጣት
< #ማርያም> ማለት < #ፍጽምት ማለት ነው>። #መልክ #ከደም #ግባት አስተባብራ ተገኝታለችና ፍጻሜው ግን #ንጽሐ ሥጋ #ንጽሐ ነፍስ #በድንጋሌ ሥጋ #በድንጋሌ ነፍስ አስተባብራ ተገኝታለችንና ብንል #በወንጌል እንደተገለጸው #መግደላዊት #ማርያም #ድንግል አልነበረችም።

▶️ ሌላውንም #ትርጉም ብናይ (ጸጋ ወሀብት) ለሰው ሁሉ #ጸጋ ሆና #ተሰታለችና#የመንግስተ #ሰማይም #መሪ ናት፤ " #ከፈጣሪ በታች #ከፍጡራን በላይም ነች"፤ #ለሰውና #ለእግዚአብሄር #ተላኪ ናት ብንል፤ ምኗ #ለሰው #ሁሉ #ጸጋ ሆኖ #እንደተሰጠ፣ ማንንስ #መንግስተ #ሰማይ #መርታ እንዳስገባች፣ #ከፍጡራን በላይ ያደረጋትስ ምንድነው ብንል #ሊቃውንት ነን የሚሉ ሰዎች #የተምታታና #የተጋጨ ወይም #የእፍረት መልስ ካልሆነ በቀር #መልስና #ማስረጃ የሌለው ነገር ነው። በመሆኑም ከላይ እንደተጠቀሰውም " #ማርያም" የሚለውን #የስም ትርጉም ለሌሎች " #ማርያም" ለተባሉ ሴቶች #ትርጉሙን ብንሰጠው #የማያስኬድና #ስህተት ሆኖ እናገኘዋለን።

️የስም #ለውጥ ባይኖረውም ብቻ #ትርጉሙ የሚሰራው ለጌታችን እናት #ለድንግል #ማርያም ብቻ ነው #ብንል #እንኳን
" ማርያም << #ፍጽምት በስጋም በነፍስም ነች>> ማለት #ጻድቅ #የለም አንድስኳ {ሮሜ 3፥11} ከተባለው እና ከሌሎች #የመጽሀፍቅዱስ ክፍሎች ጋር የሚቃረን ይሆናል።
በምድር ላይ #ኃጢአትን አላደረኩም፤ #የውርስ #ኃጢአት የለብኝም የሚል #ፍጹም ወይም #ፍጽምት ቢገኝ ኖሮ #ክርስቶስ ራሱ #መምጣት ባላስፈለገው ነበር።

▶️ ሁለተኛውን ትርጉም ደሞ ብናይ #ጸጋና #ሀብት ሆኖ #ለምድር የተሰጠው፤ የተዘጋውንም #የገነትን #ደጅ #በከበረ ሞቱ ከፍቶ #ከተሰቀለው #ወንበዴ አንዱን እንኳ #እየመራ #መንግስተ #ሰማያት ያስገባ፤ #በእግዚአብሄርና #በሰው መካከል ሆኖ #የመካከለኛ አገልግሎት #የሰጠውና #የሚሰጠው ጌታችን መድሃኒታችን #ኢየሱስ እንጅ ሌላ #ማንም አይደለም። ለዚህም እባክዎትን #መጽሀፍ #ቅዱስዎትን ገልጠው እነዚህን #የተጠቀሱ ጥቅሶችን ያንብቡ። {ቲቶ 2፥11-14፣ ኤፌ 2፥8፣ ሮሜ 5፥17፣ ዩሐ 3፥16፣ ሉቃ 23፤ 42-43፣ 1ጢሞ 2፥5፣ ዕብ 7፥24}።

▶️ ሌሎች #ሊቃውንትና #ተርጓሚዎችም << ማርያም ማለት በዚህ ዓለም #ከሚመገቡት ሁሉ #ምግብ #ለአፍ የሚጥም #ለልብ የሚመጥን < #ማር> ነው፤ #በገነትም #በህይወት ለተዘጋጁ #ጻድቃንና #ቅዱሳን < #ያም> የሚባል #ምግብ አላቸው፤ ስለዚህ ሁለቱን < #ማር" እና #ያም> የተባሉትን #ሁለት ፊደላት ስናገጣጥማቸው #ማርያም የሚል ስም #ተገኝቷል ምክንያቱም #እናትና #አባቷ አንቺ ከዚህም ኩሉ #የበለጥሽ #ጣፋጭ #የከበርሽ ነሽ ሲሉ #ማርያም ብለዋታል>> ይላሉ።

▶️ አሁንም ሌላ #ትርጉማቸውን ይቀጥሉና " #ማርያም ማለት #ሠረገላ #ፀሐይ ማለት ነው፤ #መንግስተ #ሰማያት ታገባለችና ፤ አንድም #ማርያም ማለት #ውኅብት #ወስጥወት (የተሰጠች) ማለት ነው፤ እመቤታችን እግዚእትነ ማርያም የተወለደች ዕለት በአባት እናቷ ቤት ውኅብት ወስጥወት ሆና ተገኝታለች፤ ኋላም በዓለሙ ሁሉ #አማላጅ ሆና #ሞታለችና ስለዚህ ውኅብት ወስጥወት (የተሰጠች) ናት" ይላሉ[3]።

️አሁንም እነዚህ #ሁለት #ትርጉሞች የአንድ ሰውን #የጌታችን የመድሃኒታችን #የኢየሱስ #ክርስቶስን #እናት #ድንግል #ማርያምን #ማእከል ያደረገ እንጅ ሌሎቹን #የማርያምን #ስም የያዙትን #ሴቶች ያገናዘበ አይደለም። ሆኖም ግን #የአማርኛውን ፊደል ወይም #ሐረግ ብቻ ተከትሎ < #ማር> እና < #ያም> በሚል የተከፋፈለ #ትርጉም መስጠት #አዋጭነት የለውም። ምክንያቱም ስያሜው #የእብራይስጥ #ቋንቋ እንጅ #የአማርኛ ወይም #የግእዝ አይደለም። እንደዛም እንኳን ቢሆንና ብንወስደው < #ያም> የሚባል #ቅዱሳኑ የሚበሉት #ምግብ አለ" ስለተባለው ሁኔታ #መጽሀፍ #ቅዱስም ሆነ ሌሎች መጽሀፍት #በሰማይ #ምግብ እንዳለ አይናገሩም። እንደውም #መጽሀፍ ቅዱስ #እግዚአብሔር #ምግቦችን ሁሉ #በምድር እንዳደረገ ነው የሚናገረው። {ዘፍ 1፤29-31} በተጨማሪም #የእግዚአብሔር ቃል << #መብል #ለሆድ ነው #ሆድም #ለመብል ነው እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንንም #ያጠፋቸዋል>> ይላል {1ቆሮ 6-13}።
በመሆኑም #መብል የእግዚአብሔር ዘላለማዊ #እቅዱ ስላልሆነ #በመንግስተ #ሰማያት አስቤዛ መግዛት መለዋወጥ ምግብ ማብሰል ... የለም፤ #አይኖርምም#አልተጻፈምም። በመሆኑም < #ማር" እና " #ያም> ብሎ ከፋፍሎ #የስም #ትርጉም መስጠቱ #ትርጉም የለሽ ይሆናል።

▶️ ሌላው << #ለዓለሙ ሁሉ #አማላጅ ሆና #ሞታለችና #ማርያም ማለት #ስጦታ ማለት ነው>> ብሎ መናገርና መጻፍ #ስለበደላችንና #ስለሐጢአታችን #በቀራኒዮ #መስቀል አደባባይ ላይ #የሞተውን ለይቶ #አለማወቅ ወይም #ክህደት ነው። #ለዓለም ሁሉ #ኃጢአት #አስታራቂ እንዲሆን የተሰጠንና ከአባቱም ጋር #ያስታረቀን ስለበደላችን #የሞተልን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ብቻና ደግሜ እላለሁ #ብቻ ነው። {1ጢሞ 1፥15፣ ሮሜ 3፥23፣ ሮሜ 5፥8፣ ሮሜ 8፥34፣ ዕብ 7፥24}።
ይህን ያዩ ሌሎች #ሴቶች በዚህ ወራት አምላክ #ከድንግል #ይወለዳል የተባለው ከአንቺ ይሆንን? ብለው ዘበቱባት። ወዲያው #መልአኩ መጥቶ #ትጸንሲ (ትጸንሻለሽ) አላት ዝም ብላ ሄደች። ከቤትም ደርሳ ውሃውን ስታወርድ #ትጸንሲ (ትጸንሻለሽ) አላት ይህ ነገር ደጋገመኝ #ከቤተመቅደስ ሄጄ ልረዳው ብላ #ከደናግለ #እስራኤል ጋር ተካፍላ እያስማማች የምትፈትለው #ሐርና #ወርቅ ነበር። ያንን ይዛ ሄደች #ከቤተ #መቅደስ ተቀምጣ #ሐርና #ወርቁን እያስማማች ስትፈትል #መልአክ መጥቶ #ትጸንሲ (ትጸንሻለሽ) አላት እፎኑ ይከውነኒ ዝንቱ እንዝ ኢያአምር ብእሴ - #ወንድ #ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል? አለች። እኔ ይህን አላደርገውም #እንደምን #ይሆናል ስትለው ነው ከዚህ ቡኋላ መንፈሰ እግዚአብሔር ቅዱስ ይመጽእ ላእሌኪ - ቅዱስ #የእግዚአብሔር #መንፈስ #በአንቺ ላይ #ይመጣል አላት። ይኮነኒ በከመ ትቤለኒ (እንደ ቃልህ ይሁንልኝ) አለችው። ይህን #ቃሏን ምክንያት አድርጎ #በማህጸኗ ተቀርጾአል[4]>> ብለው ያቀርባሉ።

▶️ የዚህ #ተረት #ፈጣሪ #በመጽሐፍ ቅዱስ #በዮሴፍ ቤት #ናዝሬት #ከተማ ነበረች የሚለውን #የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ #ገለጻ በመተው ሌላ #ያልነበረና የሌለ #ታሪክ ጽፏል። ይህ ደግሞ በቃሉ ላይ #አመጽና #መሸቃቀጥን ያመለክታል። አዎን ቅዱስ #ገብርኤል #ማርያምን ሲያበስራት #በእጮኛዋ #ዮሴፍ ቤት #በናዝሬት ከተማ ነበረች እንጂ #ቤተ መቅደስ ወይም #በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ አልነበረችም #ወቅቱና #ሁኔታውም አይፈቅድም {ሉቃ 1፥26}።

▶️ አንዳንዶችም #በቤተ መቅደስ ነበረች የሚለውን #አባባል #መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም ብለው #በመቃወም #ማርያም የነበረችው #በቤተ መቅደስ #ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ሳይሆን #በቤተ መቅደሱ ግቢ #በማህደረ #ደናግል ውስጥ ትኖር ነበር የሚሉ አሉ። ነገር ግን #ሄሮድስ በሰራው #ቤተ መቅደስ #አደባባይ ጊቢ ውስጥ ይኖሩና ቆመው #ለአፍታ ያህል ይጸልዩ የነበሩት #አሮጊቶችና #መበለቶች እንደነ #ሃና #የሳሙኤል እናት {1ኛ ሳሙ 1፥9 እና አሮጊቷ ሃና} ሉቃ 2፤ 36-38} እንጂ #ደናግል ወጣት #ሴቶች በጭራሽ አይገቡምና ይህም #ጥናቱ ያላላቀ #ጅምር #አንካሳ #ሃሳብ ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ ፍትህ መንፈሳዊ አንቀጽ 1 ዲድስቅሊያ 44።

📚፤ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ፤ <ስርዓተ ቤተ ክርስቲያን 3ኛ ዕትም፡ ብራና ማተሚያ ድርጅት፤ አ.አ፥ ገጽ 18፡ 1995 ዓ.ም።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፡ "ፍትሐ ነገስት ንባቡና ትርጓሜ፤ አንቀጽ 1፤ 13፡ ገጽ 23፤ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፡ አ.አ፡ 1990 ዓ.ም።

[2] 📚፤ ኢንተርናሽናል መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፤ መጽሐፍ ቅዱስ አዲሱ መደበኛ ትርጉም፤ የሉቃስ 2፥4 እና 22 ማብራርያ፡ ገጽ 1531-1532፡ 1993 ዓ.ም።

[3] 📚፤ አባ ቤተማሪያም እና መዘምራን ሞገስ ዕቁባ ጊዮርጊስ፤ "አምስቱ አዕማደ ምሥጢር ምስል ሥነፍጥረት አንድምታ"፤ አክሱም ማተሚያ ቤት፤ አክሱም፡ ገጽ 36፤ 1991 ዓ.ም።

📚፤ አስረዳ ባያብል (ሊቀ ጠበብት)፤ "ማህሌተ ጽጌ ትርጓሜ"፤ አ.አ፡ ገጽ 80፤ 1998 ዓ.ም።

[4] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ "ውዳሴ ማርያም ንባቡና አንድምታው" ዘሰንበተ ክርስቲያን፤ ገጽ 210፥ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1983 ዓ.ም።

(7.4▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat
▶️ የማርያም #መጻሕፍት አብዛኞቹ እንደነ <<ውዳሴ ማርያም>>፣ <<ቅዳሴ ማርያም>> የመሳሰሉት #የእግዚአብሔርን ቃል ወስደው ወደ #ማርያም የማጠጋጋት #ባህሪ አላቸው። በሌላ በኩል ደግሞ #የተጋነኑና #አሳፋሪ #ሐሰት ይገኝባቸዋል። #የእግዚአብሔር ቃል #እውነትን በእጅጉ ይቃረናሉ ለምሳሌ <<መጽሐፈ አርጋኖን[1]>> የተባለው ፦

〽️ <<አዳም ከልጆቹ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12 ክፍል 8፤ ቁ.6]
〽️ <<ኖህ ከልጆቹ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12 ክፍል 8፤ ቁ.9]
〽️ <<አብርሃም ከሳራ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.10]
〽️ <<ይስሐቅ ከርብቃ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.11]
〽️ <<ዕብራዊው ያዕቆብም ከልጁ ከይሁዳ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.14]
〽️ <<ሙሴ ከእስራኤል ልጆች ሁሉ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.20]
〽️ <<ዳዊት ከመዘምራን ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.23]
〽️ <<ማህበረ መላዕክት ያመሰግኑሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.26]
〽️ <<ማህበረ ነብያት ሁሉም ያመሰግኑሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.27]

▶️ እነዚህ የተጠቀሱ #የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ሲሆኑ ክፍሎቹን ወደ #መጽሐፍ ቅዱስ ሄደን #በጥሞና ብናነባቸው የሚነግሩን፦ #አዳም #ከልጆቹ ጋር #እግዚአብሔርን እንጂ #ማርያምን አላመሰገነም። ጭራሽ #አይተዋወቁም። በመካከላቸው ያለው #የዘመን ልዩነት #የሰማይና #የምድር ርቀት ያክል ነውና። [ዘፍ 4፥3፣ ዘፍ 5፤ 1-5]። #ኖህ ከልጆቹ ጋር [ዘፍ 6፥9፣ ዘፍ 8፤ 20-22፣ ዕብ 11፥7] #አብርሃም ከሣራ ጋር [ዘፍ 28፥8፣ ዘፍ 21፥1፣ ዕብ 11፥8፣ 19] #ይስሐቅ #ከርብቃ ጋር [ዘፍ 27፥27]፣ #ያዕቆብም [ዘፍ 28፤ 18-22፣ ዕብ 11፥20]፣ #ሙሴ #ከእስራኤላውያን ጋር [ዘጸ 15፤ 1-26፣ ዕብ 11፤ 23-28]፣ #ዳዊትም [2ሳሙ 6፤ 12-33፣ መዝ 8፤ 1-9] #ማህበረ #መላእክትም [ኢሳ 6፥3፣ ራዕ 4፤ 7-11]። #የሐዋርያት ማህበርም [ሐዋ 2፤ 46-47፣ ሐዋ 16፥25]፣ ሁሉም በግልጽ #እግዚአብሔርን ብቻ እንዳከበሩ እንጂ #ማርያምን ያመሰግኑበትም ሆነ #ስሟን እንኳን የጠሩበት አንድም #ቦታ የለም።

▶️ ስለሆነም <<ማርያምን ያመሰግናሉ>> የሚለው #ኢ-መጽሐፍቅዱሳዊና #የነብያትን#የመላእክትን፣ እንዲሁም #የሐዋርያትን ስም ማጥፋትና #ለእግዚአብሔር ያቀረቡትን የተባረከ #ምስጋናቸውን ወደራስ #ሃሳብና #መሻት ለመጠምዘዝ የተደረገ ከንቱ #የባእድ #አምልኮ #ሙከራ ነው።

ሌላው #ውሸት የታጨቀበት #መጽሐፍ ደግሞ <<መጽሐፈ ሰዓታት[2]>> የተባለው #መጽሐፍ ነው። ለምሳሌ ያክል

〽️ <<ለመጸብሐዊ ማቴዎስ እንተ ረሰይኪዩ ወንጌላዊ - ለቀራጩ ማቴዎስ ወንጌላዊ ያደረግሽው አንቺ ነሽ>> ይላል [መጽሐፈ ሰዓታት ርኅርኅተ ህሊና ገጽ 132 - 133]። ነገር ግን #ማቴዎስ ወደ #ወንጌላዊነት እንዴት እንደመጣ #ራሱ #ስለራሱ ሲናገር <<ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና። ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።>> [ማቴ 9፥9] ብሏል። ይህንን #መጽሐፍ ቅዱሳዊ #እውነት ክዶ #ማርያም #ማቴዎስን #ወንጌላዊ አደረገችው ማለት ምን ይሉታል?

▶️ ማህሌተ ጽጌ የተባለው #መጽሐፍ ደግሞ <<ቅዱስ ጴጥሮስ በ30 እስታቴር (በ30 ብር) በርተሎሜዎስን ለግብርና ስራ ሸጠው>> ይላል። በመቀጠልም <<የጴጥሮስ ጥላው የጳውሎስም ልብሱ ማርያም አንቺ ነሽ>> ይላል። አንባቢ ሆይ አረ #እናስተውል!!። ሐዋርያው #ጴጥሮስ ሐዋርያው #በርተሎሚዎስን እንደሸጠ ከየት የተገኘ #ወሬ ነው?። #ከታሪክ አንጻር እንኳን ብንመለከተው #ጴጥሮስም #በርተሎሚዎስም #ለወንጌል አገልግሎት ከመጠራታቸው በፊት #በሮማ ግዛት ስር የነበሩ ተራ #አይሁዳውያን ነበሩ እንጂ #ሰውን የሚሸጡ #ገዢዎች እንኳ አልነበሩም። ታድያ ሐዋርያው #ጴጥሮስ የወንጌል ጓደኛውን #በርተሎሜዎስን #ለግብርና ስራ #በ30 ብር ሸጠ ማለትና #የጴጥሮስ ጥላው #የጳውሎስም የልብሱ ዘርፍ #በሽተኞችን ሲፈውስ #ፈዋሹ #እግዚአብሔር ብቻ ሆኖ ተጽፎ እያለ <<ጥላና ልብሱ ማርያም ነበረች>> ማለት አያሳተዛዝብም? [ሐዋ 5፤ 15-16፣ 19፤ 11-12]። አረ ያስተዛዝበናል!

▶️ ይህ በብዙ የሳተ #መጽሐፍ #በግእዝና #በዜማ ለህዝቡ ስለሚቀርብለት አብዛኛው #ቋንቋውን ስለማያውቅ የሚባለውን #ሳይሰማና #ሳያስተውል #አሜን ብሎ ይሄዳል። ምናልባት ጉዳዩን በጥሞና #መረዳት ቢችልና ለማረም ቢሞክር ደግሞ #ተሐድሶ#መናፍቅ ወ.ዘ.ተ ተብሎ #የውግዘት ናዳው ይዘንብበታልና አብዛኛው #ዝም ማለቱን የመረጠ ይመስላል።

<<ሰውም ሁሉ ባልንጀራውን ያታልላል በእውነትም አይናገርም፤ ሐሰትን መናገርንም ምላሳቸው ተምሮአል፥ ክፉንም ለማድረግ ይደክማሉ። ማደሪያህ በሽንገላ መካከል ነው፥ ከሽንገላም የተነሣ እኔን ያውቁኝ ዘንድ እንቢ ብለዋል፥ ይላል እግዚአብሔር።>> [ኤር 9፤ 5-6]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ አርጋኖን የእመቤታችን ምስጋና፤ ተስፋ ገብረስላሴ ማተሚያ ቤት፡ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።

[2] ሰፊ ማብራሪያ
📚፤ GBV <መጽሀፈ ሰአታት በመቅደሱ ሚዛን> 2ተኛ ዕትም ጥቅምት፡ 1995 ዓ.ም፤ BGNLJ፤ አ.አ፥ ኢትዮጵያ።
ይመልከቷል።

@gedlatnadersanat
(8.6.6▶️) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat