ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ብዙ ሴቶች #ማርያም በሚል ስም ይጠራሉ[1]። [ለምሳሌ]👇

〽️ 1፦ "የሙሴ እህት ማርያም"
/ዘጸ 2፥4-8/

▶️ የዚችን #ማርያም ታሪክ #በመጽሀፍቅዱስ ውስጥ ስናይ #ወንድሟ #ሙሴ በወንዝ #ዳር #በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን #ለማወቅ ስትመለከት ወደ ወንዙ የመጣችውን #የፈርኦንን #ልጅ #በጥበብ አነጋግራና #እንድታጠባው የገዛ #እናታቸውን #በሞግዚትነት ስም አገናኝታ ወንድሟ #ሙሴ እንዲያድግ #አስተዋጽኦ ያደረገች ናት። #ሙሴም በዚህ እድልና በእግዚአብሄር #አላማ አድጎ #እስራኤላውያንን #የኤርትራን #ባህር ካሻገራቸው በኋላ #ነብይት ሆና #ሴቶችን #በመዝሙርና #በምስጋና መርታለች {ዘጸ 15፥20}። ከዛ ግን #ማርያም #የሙሴን የበላይነት ካለመውደዷ የተነሳ #ኢትዮጵያዊት #ሚስቱን ምክንያት አድርጋ #አማችው#እግዚአብሔር ግን #በለምጽ #ቀጣት {ዘኅ 12 ; ዘዳ 24፥9}። በመጨረሻም #እስራኤላውያን ገና በጉዞ ሳሉ #በቃዴስ #በረሃ #ሞተች በዚያው #ተቀበረች። {ዘኅ 20፥1}።

〽️ 2፦ "የዩቴር ልጅ የዕዝራ የልጅ ልጅ ማርያም" {1ዜና 4፥17} ፦

▶️ የዚች #ማርያም ታሪክና ተግባሯ ብዙም አልተጠቀሰም

〽️ 3፦ "የጌታችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም" {ሉቃ 1፤ 26-27} ፦

▶️ ሙሉ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ታሪኳ <13🌐☑️ ቅድስት ድንግል ማርያም በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ> በሚለው ርእስ ስር ይቀርባል።

〽️ 4፦ "የማርታና የዓላዛር እህት ማርያም" {ዩሐ 11፥1} ፦

▶️ ከኢየሩሳሌም አጠገብ ባለው #ቢታንያ በተባለው #መንደር #ከእህቷ #ማርታና ከወንድሟ #አላአዛር ጋር ትኖር ነበር። አንድ ቀን #ጌታችን #ኢየሱስ #ክርስቶስም ወደ ቤታቸው ሄዶ ሲጠይቃቸው ይህቺ #ማርያም ወደ እርሱ #ቀርባ ቃሉን #በጽሞና #ስለሰማችና #ስለተማረች #ክርስቶስ አመስግኗታል {ሉቃ 10፤ 39-42}። ወንድሟ #አላአዛርም #ከሙታን በተነሳ ጊዜ #ከጌታ #ኢየሱስ ጋር ብዙ ተነጋግራለች {ዩሐ 11}። ቀድም ብሎም ይቺ #ማርያም #ጌታችን እንደሚሞት አውቃ #በናርዶስ #ሽቶ #እግሩን ቀብታውም ነበር። {ዩሐ 12፤ 1-8}።

〽️ 5፦ "መግደላዊት ማርያም"፦

▶️ ጌታችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ሰባት #አጋንንት ከእርሷ ካወጣላት ቡኃላ ታገለግለው ነበር {ሉቃ 8፥2 , ማር 15፥40}። ይህቺ #ሴት ለክርስቶስ #መሰቀልና #መነሳት #ምስክር ነበረች {ማቴ 27፤፦55 ፣ 56 ፣ 61, ማር 15፤ 40-47 ፣ ዩሐ 19፤25 ፣ ማቲ 28፤ 1-10 ፣ ማር 16፤ 1-8፣ ሉቃ 24፤10}። #ከትንሳኤውም ቡሀላ #በአትክልት ቦታ ለብቻዋ #ክርስቶስን #ካየችውና #ካነጋገረችው ቡሀላ የመጀመሪያዋ #ትንሳኤውን #መስካሪ ሆናለች {ዩሐ 20፤ 1-18}።

〽️ 6፦ "የቀለዩጳ ሚስት ማርያም "፤

▶️ ጌታ በተሰቀለ ጊዜ #ከመስቀሉ #አጠገብ ቆማ ነበር {ዩሐ 19፤25}።

〽️ 7፦ "የማርቆስ እናት ማርያም"፤

▶️ ሐዋሪያት ተሰብስበው በቤቷ #ይጸልዩና #ይመካከሩ ነበር {ሐዋ 12፥12}።

እንደምናየው #በመጽሀፍቅዱስ ውስጥ #ብቻ #ማርያም ተብለው የሚጠሩ #ሰባት #ሴቶች አሉ። #እስራኤላውያንም #ለልጆቻቸው #ስም ሲያወጡም ሆነ #ለራሳቸው የሆነ #ስያሜ #ሲመርጡ ከልዩ #የሕይወት #ታሪካቸው ጋር #የተያያዘውን ነው።
አንዳንዶች በተለይ " #ማርያም" የሚለውን ስም #የጌታችን #የኢየሱስ #ክርስቶስን #እናት ብቻ #ማእከል አድርገው በሚገርም ሁኔታ #ተርጉመው #ሌላ #ትምህርት ለዛውም #ከእግዚአብሄር #ብቸኛ የማዳን #ተግባር ጋር #የሚጋጭ አርገው እንዲህ ተርጉመውታል።👇👇

🔆 1ኛ ትርጉም፦

" #ማርያም" ማለት " #ፍጽምት" ማለት ነው። መልክ ከደም ግባት አስተባብራ ተገኝታለችና ፍጻሜው ግን #ንጽሐ ሥጋ #ንጽሐ ነፍስ #በድንጋሌ ሥጋ #በድንጋሌ ነፍስ አስተባብራ ተገኝታለችና።

🔆 2ኛ ትርጉም፦

" #ማርያም" ማለት #ጸጋ #ወሀብት(ጸጋና ሀብት) ማለት ነው። #ለእናት #ለአባቷ #ጸጋ ሆና ተሰጣለች ፍጻሜው ግን ለሰው ሁሉ #ጸጋ ሆና #ተሰጥታለች

🔆 3ኛ ትርጉም፦

" #ማርያም" ማለት #መርሕ #ለመንግሥተ ሰማያት(የመንግሥተ ሰማያት መሪ) ማለት ነው። ምዕመናንን መርታ #ገነት #መንግስተ #ሰማያት አግብታለችና።

🔆 4ኛ ትርጉም፦

"ማርያም" ማለት #ልዕልት ማለት ነው። #መትሕተ ፈጣሪ #መልዕልተ ፍጡራን(ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ) ይሏታልና።

🔆 5ኛ ትርጉም፦

ተላአኪተ እግዚአብሔር ወሰብእ {#የእግዚአብሄርና #የህዝብ #ተላኪ ማለት ነው።[2]
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ብዙ ሴቶች #ማርያም በሚል ስም ይጠራሉ[1]። [ለምሳሌ]👇 〽️ 1፦ "የሙሴ እህት ማርያም" /ዘጸ 2፥4-8/ ▶️ የዚችን #ማርያም ታሪክ #በመጽሀፍቅዱስ ውስጥ ስናይ #ወንድሟ #ሙሴ በወንዝ #ዳር #በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን #ለማወቅ ስትመለከት ወደ ወንዙ የመጣችውን #የፈርኦንን #ልጅ #በጥበብ አነጋግራና #እንድታጠባው የገዛ #እናታቸውን #በሞግዚትነት ስም አገናኝታ…
▶️ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ለ"ማርያም" ለሚለው ስም የተሰጡ #ትርጉሞች #የቤተስክርስቲያን #አባቶችም ሆኑ #ወጣት #ሰባኪያንና #ህዝቡም በብዛት የሚያውቁት #የተለመደ #ትርጉም ነው። የሚገርመው ደሞ #የስሙ #ትርጉሞች ብዙ #ማርያም የተባሉ #ሴቶች እያሉ ማእከል ያደረገው ግን #የጌታችን #እናት #ድንግል #ማርያምን ብቻ ይመስላል። እነዚን #ትርጉሞች ይዘን ለሌሎች < #ማርያም> ለተባሉ #ሴቶች ትርጉሙን ብንሰጣቸው #የትርጉሙ #ባለቤቶች ራሱ #ይሸማቀቁበታል። [ለምሳሌ]፦
#በስም #ደረጃ ከክርስቶስ እናት ጋር #ምንም #ልዩነት ላልነበራት #ለመግደላዊት #ማርያም ትርጓሜውን ብንሰጣት
< #ማርያም> ማለት < #ፍጽምት ማለት ነው>። #መልክ #ከደም #ግባት አስተባብራ ተገኝታለችና ፍጻሜው ግን #ንጽሐ ሥጋ #ንጽሐ ነፍስ #በድንጋሌ ሥጋ #በድንጋሌ ነፍስ አስተባብራ ተገኝታለችንና ብንል #በወንጌል እንደተገለጸው #መግደላዊት #ማርያም #ድንግል አልነበረችም።

▶️ ሌላውንም #ትርጉም ብናይ (ጸጋ ወሀብት) ለሰው ሁሉ #ጸጋ ሆና #ተሰታለችና#የመንግስተ #ሰማይም #መሪ ናት፤ " #ከፈጣሪ በታች #ከፍጡራን በላይም ነች"፤ #ለሰውና #ለእግዚአብሄር #ተላኪ ናት ብንል፤ ምኗ #ለሰው #ሁሉ #ጸጋ ሆኖ #እንደተሰጠ፣ ማንንስ #መንግስተ #ሰማይ #መርታ እንዳስገባች፣ #ከፍጡራን በላይ ያደረጋትስ ምንድነው ብንል #ሊቃውንት ነን የሚሉ ሰዎች #የተምታታና #የተጋጨ ወይም #የእፍረት መልስ ካልሆነ በቀር #መልስና #ማስረጃ የሌለው ነገር ነው። በመሆኑም ከላይ እንደተጠቀሰውም " #ማርያም" የሚለውን #የስም ትርጉም ለሌሎች " #ማርያም" ለተባሉ ሴቶች #ትርጉሙን ብንሰጠው #የማያስኬድና #ስህተት ሆኖ እናገኘዋለን።

️የስም #ለውጥ ባይኖረውም ብቻ #ትርጉሙ የሚሰራው ለጌታችን እናት #ለድንግል #ማርያም ብቻ ነው #ብንል #እንኳን
" ማርያም << #ፍጽምት በስጋም በነፍስም ነች>> ማለት #ጻድቅ #የለም አንድስኳ {ሮሜ 3፥11} ከተባለው እና ከሌሎች #የመጽሀፍቅዱስ ክፍሎች ጋር የሚቃረን ይሆናል።
በምድር ላይ #ኃጢአትን አላደረኩም፤ #የውርስ #ኃጢአት የለብኝም የሚል #ፍጹም ወይም #ፍጽምት ቢገኝ ኖሮ #ክርስቶስ ራሱ #መምጣት ባላስፈለገው ነበር።

▶️ ሁለተኛውን ትርጉም ደሞ ብናይ #ጸጋና #ሀብት ሆኖ #ለምድር የተሰጠው፤ የተዘጋውንም #የገነትን #ደጅ #በከበረ ሞቱ ከፍቶ #ከተሰቀለው #ወንበዴ አንዱን እንኳ #እየመራ #መንግስተ #ሰማያት ያስገባ፤ #በእግዚአብሄርና #በሰው መካከል ሆኖ #የመካከለኛ አገልግሎት #የሰጠውና #የሚሰጠው ጌታችን መድሃኒታችን #ኢየሱስ እንጅ ሌላ #ማንም አይደለም። ለዚህም እባክዎትን #መጽሀፍ #ቅዱስዎትን ገልጠው እነዚህን #የተጠቀሱ ጥቅሶችን ያንብቡ። {ቲቶ 2፥11-14፣ ኤፌ 2፥8፣ ሮሜ 5፥17፣ ዩሐ 3፥16፣ ሉቃ 23፤ 42-43፣ 1ጢሞ 2፥5፣ ዕብ 7፥24}።

▶️ ሌሎች #ሊቃውንትና #ተርጓሚዎችም << ማርያም ማለት በዚህ ዓለም #ከሚመገቡት ሁሉ #ምግብ #ለአፍ የሚጥም #ለልብ የሚመጥን < #ማር> ነው፤ #በገነትም #በህይወት ለተዘጋጁ #ጻድቃንና #ቅዱሳን < #ያም> የሚባል #ምግብ አላቸው፤ ስለዚህ ሁለቱን < #ማር" እና #ያም> የተባሉትን #ሁለት ፊደላት ስናገጣጥማቸው #ማርያም የሚል ስም #ተገኝቷል ምክንያቱም #እናትና #አባቷ አንቺ ከዚህም ኩሉ #የበለጥሽ #ጣፋጭ #የከበርሽ ነሽ ሲሉ #ማርያም ብለዋታል>> ይላሉ።

▶️ አሁንም ሌላ #ትርጉማቸውን ይቀጥሉና " #ማርያም ማለት #ሠረገላ #ፀሐይ ማለት ነው፤ #መንግስተ #ሰማያት ታገባለችና ፤ አንድም #ማርያም ማለት #ውኅብት #ወስጥወት (የተሰጠች) ማለት ነው፤ እመቤታችን እግዚእትነ ማርያም የተወለደች ዕለት በአባት እናቷ ቤት ውኅብት ወስጥወት ሆና ተገኝታለች፤ ኋላም በዓለሙ ሁሉ #አማላጅ ሆና #ሞታለችና ስለዚህ ውኅብት ወስጥወት (የተሰጠች) ናት" ይላሉ[3]።

️አሁንም እነዚህ #ሁለት #ትርጉሞች የአንድ ሰውን #የጌታችን የመድሃኒታችን #የኢየሱስ #ክርስቶስን #እናት #ድንግል #ማርያምን #ማእከል ያደረገ እንጅ ሌሎቹን #የማርያምን #ስም የያዙትን #ሴቶች ያገናዘበ አይደለም። ሆኖም ግን #የአማርኛውን ፊደል ወይም #ሐረግ ብቻ ተከትሎ < #ማር> እና < #ያም> በሚል የተከፋፈለ #ትርጉም መስጠት #አዋጭነት የለውም። ምክንያቱም ስያሜው #የእብራይስጥ #ቋንቋ እንጅ #የአማርኛ ወይም #የግእዝ አይደለም። እንደዛም እንኳን ቢሆንና ብንወስደው < #ያም> የሚባል #ቅዱሳኑ የሚበሉት #ምግብ አለ" ስለተባለው ሁኔታ #መጽሀፍ #ቅዱስም ሆነ ሌሎች መጽሀፍት #በሰማይ #ምግብ እንዳለ አይናገሩም። እንደውም #መጽሀፍ ቅዱስ #እግዚአብሔር #ምግቦችን ሁሉ #በምድር እንዳደረገ ነው የሚናገረው። {ዘፍ 1፤29-31} በተጨማሪም #የእግዚአብሔር ቃል << #መብል #ለሆድ ነው #ሆድም #ለመብል ነው እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንንም #ያጠፋቸዋል>> ይላል {1ቆሮ 6-13}።
በመሆኑም #መብል የእግዚአብሔር ዘላለማዊ #እቅዱ ስላልሆነ #በመንግስተ #ሰማያት አስቤዛ መግዛት መለዋወጥ ምግብ ማብሰል ... የለም፤ #አይኖርምም#አልተጻፈምም። በመሆኑም < #ማር" እና " #ያም> ብሎ ከፋፍሎ #የስም #ትርጉም መስጠቱ #ትርጉም የለሽ ይሆናል።

▶️ ሌላው << #ለዓለሙ ሁሉ #አማላጅ ሆና #ሞታለችና #ማርያም ማለት #ስጦታ ማለት ነው>> ብሎ መናገርና መጻፍ #ስለበደላችንና #ስለሐጢአታችን #በቀራኒዮ #መስቀል አደባባይ ላይ #የሞተውን ለይቶ #አለማወቅ ወይም #ክህደት ነው። #ለዓለም ሁሉ #ኃጢአት #አስታራቂ እንዲሆን የተሰጠንና ከአባቱም ጋር #ያስታረቀን ስለበደላችን #የሞተልን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ብቻና ደግሜ እላለሁ #ብቻ ነው። {1ጢሞ 1፥15፣ ሮሜ 3፥23፣ ሮሜ 5፥8፣ ሮሜ 8፥34፣ ዕብ 7፥24}።