ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
የአገራችን ቅዱሳን እውን መንፈሳዊ ናቸው ?? #በአገራችን ቅዱሳን ተብለው ታቦት ተቀርጾ -ቀን ተሰይሞ -ገድል ተጽፎላቸው ቃል ኪዳን ተቀብለዋል እየተባሉ ከወር እስከወር የሰው ልብ ላይ ነግሰው የአምላክ ገንዘብ የሆነውን ስግደትና ዝማሬ መስዋእትም በጸጋ ስም የሚኮመኩሙ የቡልጋ የትግራይና የጎጃም ተወላጅ የሆኑ አፈጣጠራቸው አኑዋኑዋራቸውና ትምህርታቸው አለም ከተፈጠረ ጀምሮ ያልተሰማ #ክንፍ…


ቅዱስ እውነት ???

#ገድለ ተክለሃይማኖት፥ 48:1- 4

" አንድ ቀን በባሕር ዳር ተቀምጦ ሳለ፥ ሰይጣን ከባሕሩ ወጣ። የአባታችንንም ደቀመዝሙር ያዘው። አንተ ርኩስ መንፈስ ከልጄ ውጣ እያለ በመስቀል ምልክት አማተበ። ሰይጣኑም ዛሩም ደቀመዝሙሩን ትቶ ፈጥኖ ሸሸ። ሊያመልጥም ወደደ። ብፁዕ አባታችንም አማተበበት። ወደ ባሕሩ ሊገባ ባይቻለው በጥልቁ ባሕር ወደብ ቆመ። ብፁዕ አባታችንም ሄዶ #በእጁ #ያዘው። ያን ጊዜ ዕጡ ወደቀና ኃይሉም ደከመና ለሁሉም በግልጥ ታየ።
“...ስምህ ማን ነው?” አለው።
"ባሕረ አልቅም።"
"እንግዲህ #ከእኔ ጋር #ትሄዳለህን ወይስ ወደ ማደሪያህ #ትመለሳለህ?” አለ።
"ከእንግዲህ ወዲህ ወደ ማደሪያዬ መመለስ አይቻለኝም። #በማማተብህ ስልጣኔን ሽረኸዋልና።" አለው።
አባታችን ተክለሃይማኖትም ወስዶ #ገረዘው፥ ወደ ፍፁም #ክርስቲያንነትም ለወጠው። ስሙንም #ክርስቶስ ኃረዮ ማለትም #ክርስቶስ የመረጠው ብሎ ጠራው። ብፁዕ አባታችንን ሲያገለግለው ኖረ። ከጥቂትም ቀን በኋላም የምንኩስናውን ልብስ አልብሶ ወደ ባዕቱ አገባው። ይህችውም ደብረ አሰቦ ናት። ሰይጣን #ሞቶ #መንግስተ ሰማያት እስኪገባ ድረስ በተረፈው ዘመኑ ሁሉ #መነኮሳትን #ደስ #የሚያሰኝ#እግዚአብሔርንም #የሚወድ ሆነ።
********

በኦርቶዶክስ ቤተ እምነት ውስጥ ያሉ #ድርሳናት#ገድላት#ሰይፈ ሥላሴ፥ #ክርስቶስ ሳምራ፥ #ገድለ ክርስቶስ፥ #ተዓምረ ማርያም፥ #መልክዓ መላዕክታት፥ #ውዳሴ ማርያም እንዲሁም በስድሳ ስድስቱ የመጽሐፍ ቅዱስ መፃሕፍት ላይ #የተጨመሩ ሌሎች መፅሐፍት መፅሐፍ ቅዱስን እጅግ የሚፃረሩ #ፀረ ክርስቶስ፣ #የደብተራ ሥጋዊና አጋንንታዊ ውጤት ናቸው።
#አጋንንት ሳቢ #ደብተራዎች የጻፉት የረከሱ ገድላት መካከል #ገድለ ተክለሃይማኖት አንዱ ነው።

እስከ መቼ ጌታ እግዚአብሔርን ነው የማመልከው እያልክ #በተክለሃይማኖት ስም የአጋንንትን ጽዋ ትጠጣለህ። እርም ባለበት መርገም አይርቅም። ልብህን ወደ እውነተኛው #የእግዚአብሔር ቃል ወደ #መፅሐፍ ቅዱስ እና ወደ ነፍስህ አዳኝ ወደ #ጌታ እየሱስ ክርስቶስ ለፍሬ በሆነ ንስሐ ተመልስ።
********

"እሁድና ሐሙስ እባብ የገደለ የክርስቲያን ወገን ሁሉ ኃጢያቱ ይሰረይለታል፤ ብለህ ለልጆችህ ንገራቸው።" ብሎ ጌታዬ እየሱስ ክርስቶስ የነገረኝን አሁንም እነግራችኋለሁ። በልባችሁ ጠብቁት።
#ገድለተክለሃይማኖት፥51፥6
********
🕇 የከበረውን የሕያው እግዚአብሔርን ቅዱስ ቃል #መፅሐፍ ቅዱስን ገለባ ከሆነውና ከረከሰው ስጋዊና አጋንንታዊ መልዕክት ጋር ምን አንድ አደረገው???
#ሰይጣንን ይዤ #ገረዝኩት#አጠመኩት#ቅስና አስተምሬ #የኦርቶዶክስ #መነኩሳትን #አገልግሎ #ሰይጣን ወደ #መንግስተ ሰማያት ገብቶዋል ብሎ እራሱ በፃፈው በገድለ ተክለሃይማኖት.48:1-4 ላይ መስክሯል።
********
#ገድለ ተክለሃይማኖት፥ 48:1- 4 :- አንድ ቀን በባሕር ዳር ተቀምጦ ሳለ፥ ሰይጣን ከባሕሩ ወጣ። ......
********
ይህ የአጋንንት ጎታቾች ክፉ ግብር እንጂ የእግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ጨርሶ አይደለም። #ሰይጣን መንግስተ ሰማያት ገብቶማ ቢሆን ኖሮ ምድር የንፁሐንና የጻድቃን ደም ባልፈሰሰባት ነበር። ዋይታና ልቅሶ፥ ረሃብና ጥማት፥ ጦርነትና ሞት ባልተገኘባት ነበር።
የተረገመው ሰይጣን ግን ኦርቶዶክስ እንደምትከተለው የተክለ ሃይማኖት የሐሰት ትምህርት በመንግሥተ ሰማያት ሳይሆን በምድርና በአየር በጥልቁም ሆኖ የአመፅ፥ የክፋት፥ የጭካኔ፥ የእርኩስት፥ የማታለልና የሐሰት ክፉ ጨካኝ ደም አፍሳሽ ስራውን በምድር ሁሉ ላይ እያደረገ ነው።
ለሰይጣን መንግስተ ሰማያት ቦታ እንደሌለ አላነበቡም ይሆን..👇

የማቴዎስ ወንጌል 25:41

በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል። እናንተ ርጉማን፥ #ለሰይጣንና ለመላእክቱ #ወደ #ተዘጋጀ ወደ #ዘላለም #እሳት ከእኔ ሂዱ።

ከዚህ በላይ #ለሰይጣን #ጠበቃና #አገልጋይ ማን ነው?
ከዚህ በላይ ምን #የተረገመና እርም ምን አለ?
ከዚህ በላይ #መናፍቅ ማን ነው?
ከዚህ በላይ #ፀረ ክርስቶስ ማን ነው?

ኦርቶዶክስ #ገድላትን#ድርሳናትን#ውዳሴያትን#መልክዓ #መላዕክትንና#ሰይፈ ሥላሴ፥ #ክርስቶስ ሳምራ፥ #ገድለ ክርስቶስ፥ #ተዓምረ ማርያም፥ ሌሎችንም #ፀረ #ክርስቶስ መጻሕፍቶቿን አቃጥላና ጥላ ልብን በትህትና በማድረግ መጽሐፍ ቅዱስን ብቻ በመከተል ተሐድሶ ማድረጓ በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ የእምነት ተከታዮቿ የዘላለም ሕይወትና ክብር ነው። ልብን እልከኛ ማድረግ ግን ጌታ እየሱስ ክርስቶስን እንደሰቀሉት ለአይሁድ ፈሪሳውያኖችም አልሆነም።

@gedlatnadersanat
👇👇
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ለ"ማርያም" ለሚለው ስም የተሰጡ #ትርጉሞች #የቤተስክርስቲያን #አባቶችም ሆኑ #ወጣት #ሰባኪያንና #ህዝቡም በብዛት የሚያውቁት #የተለመደ #ትርጉም ነው። የሚገርመው ደሞ #የስሙ #ትርጉሞች ብዙ #ማርያም የተባሉ #ሴቶች እያሉ ማእከል ያደረገው ግን #የጌታችን #እናት #ድንግል #ማርያምን ብቻ ይመስላል። እነዚን #ትርጉሞች ይዘን ለሌሎች < #ማርያም> ለተባሉ #ሴቶች ትርጉሙን…
▶️ ከላይ እንዳየነው አንዳንዶች #የስሙን ሙሉ #ሐረግ ተከትለው ሌሎች ለሁለት ከፍለው #ለመተርጎም ከሞከሩት #ውጪ ሌሎች ደግሞ ከዚህ በተለየ መንገድ #ማርያም የሚለውን ስም #ለማብለጥ ወይም #ከፍ #ለማረግ ሲሉ #ማርያም ስለሚለው #ስም #ትርጉም #የአማርኛውን ወይም #የግእዙን ሆህያት ብቻ ተከትለው #ፊደል #በፊደል እየከፋፈሉ #በግእዝ ቋንቋ #በግጥም መልክ ይተረጉማሉ።👇👇

✳️👉 ማኅደረ መለኮት [የመለኮት ማደሪያ]።
✳️👉 ርግብየ ይቤላ [ንጉስ ሰለሞን ርግቤ ያላት፥ መኃ 6፥9]።
✳️👉 ያንቀዓዱ ኅቤኪ ኩሉ ፍጥረት [ሁሉም ፍጥረት ወደ አንቺ ያንጋጥጣል(ያቀናል)]።
✳️👉 ምስአል ወምስጋድ [ወምስትሥራየ ኃጢአት፣ የምንለምናት፣ የምንሰግድላት[4]]።

️ይህም #ትርጉም ከላይ እንዳልነው #የአማርኛ #ፊደላትን #በግዕዝና #በግጥም #የመተርጎም ሙከራ ሲሆን ይህም እንደሌሎቹ #ትርጎሞች ለሌሎች " #ማርያም" የሚለው #ስም ላላቸው የሚያገለግል አይመስልም። እንዲህ አይነቱ #ትርጉም የመስጠት አካሄድ ደግሞ #ከዓውደ #መሠረቱ ያስወጣል።

️በዚህ #ትርጉም መሠረት " #ማርያም ማለት #የመለኮት #ማደሪያ የሆነች፤ ንጉስ ሠሎሞን #በመኃልይ #መኃልይ መጽሐፉ #ርግቤ ያላት፤ ፍጥረት ሁሉ ወደ እርሷ #የሚያቀኑ#የሚሰግዱ#የሚለምኑ እና እርሷም #ለምላሹ #ኃጢአትን #የምታስተሰርይ ናት" ማለት በግልጽ #ማርያምን #ማምለክ ማለት ነው። #አምልኮ ከዚህ ውጪ #ካለ ንገሩን!!

▶️ መቼም #ሰይጣን በተለይም #በኢትዮጵያ #በ15ኛው ክፍለ ዘመን ጊዜና ባለስልጣናት ገጥሞት በብዙ #ሠይፍ < #የማርያምን #ምልጃ> ትምህርት ወደ #ቤተክርስቲያን አስገብቶ #ማርያም ባትሰማቸውም ወደ እርሷ #የሚያንጋጥጡ#የሚሰግዱ#የሚለምኑ#ኃጢአታቸውን #የሚናዘዙ ይብዙ እንጅ #በመጽሀፍቅዱስ ታሪክ እንኳን #ወደእሷ ወደየትኛውም #ፍጡር #የጸለየ አናገኝም።

▶️ ደግሞ #ሰሎሞን #በመኃልየ #መኃልይ መጽሐፉ ሱናማይት{ሱናማጢሳዊት} የሆነችውን አንዲት ልጃገረድ #ውዴ#ርግቤ#መደምደሚያየ እያለ በፍቅር እንዴት #አሸንፎ ወደ ቤቱ እንዳመጣትና #ባሸበረቀ አልጋው ላይ አጋድሞ #ጡቶቿ እንዴት እንዳረኩት እርሷም በእርሱ እንዴት #እንደረካች የሚናገረውን #የፍቅር #ኃይልና ግለት #የተንጸባረቀበትን መጽሐፍ ወስዶና #በጥሶ <ሰሎሞን #ርግቤ #መደምደሚያዬ ያላት #ማርያምን ነው> ማለት ምናልባት መጽሐፉንና #ዓላማውን #ካለማንበብና #ካለማወቅ የመነጨ፣ አሳፋሪም ጭምር መሆኑን #የሱናማይቷ ሴት #ለፍቅር ስሜት የመጦዝ ባህሪ ታላቅ አድርገው ለሚገምቷት "ለቅድስት ድንግል ማርያም" ባልተስማማ ነበር።

▶️ መኃልየ #መኃልየ መጽሀፍም #የብሉይኪዳን ክፍል እንደመሆኑ #በሰለሞንና #በማርያም መካከል ያለውን "የዘመን ልዩነት" መገመት ራሱ አይከብድም። #ማርያም #በሰለሞን ዘመን ፈጽማ ያልነበረችውን፤ #ሰለሞን እንዴት በወቅቱ ከነበሩት < #ስልሳ ንግሥታት #ሰማኒያም ቁባቶች(ውሹሞች) #ቁጥር የሌላቸው ቆነጃጅቶች> ጋር #በውሽምነት መልኩ ሊቆጥራት ይችላል? {መኅልየ 6፥8}

▶️ ደግሞ < #የዓለምን #ኃጢአት ሊያስወግድ የተገለጠ #የእግዚአብሄር #በግ> {ዩሐ 1፥29 , ራዕ 5፤5-10} #ኃጢአትን #የማስተሰረይ ስልጣንም #የኢየሱስ #ክርስቶስ ብቻ እንደሆነ እያወቅን {ማር 2፤10} ማርያምን "ወምስትሥራየ ኃጢአት" {ኃጢአትን የምታስተሰርይ} እንዴት ልንል እንችላለን?? #በኃጢአት ላይ የወጣውን #የእግዚአብሄርን #ቁጣ #ፍርዱን #ሊያቃልለው ወይም #ሊያስተወው የሚችልስ ጉልበተኛ ማነው? #ሙሴ እንኳ በምድር ህይወቱ #የእስራኤልን #ኃጢአት ተከራክሮ #ለማስቀረት ቢሞክርም #እግዚአብሔር #ፍርዱን መለወጥ ባለመቻሉ በርካቶች #ሞተዋል። {ዘዳ 32፤30-35}። #ኃጢአተኛው እራሱ #ካልተመለሰና #ንስሐ ካልገባ በቀር #እግዚአብሔር ኃጢአትን ይጠላል #ይቀጣልምም {ዩሐ 8-24}።