ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.81K subscribers
536 photos
69 videos
81 files
393 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
▶️ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን #ታቦቱ ይቀመጥበት የነበረውን #ቅድስተ ቅዱሳን ስፍራ #ቤተመቅደስ ስትለው ቀጥሎ ያለውን ክፍል #ቅድስት #ሦስተኛውን ክፍል ደግሞ #ቅኔ ማህሌት ትለዋለች። በዚህም መሠረት ማርያም #ከ3 ዓመት ዕድሜዋ ጀምሮ #በቤተ መቅደስ ቅድስተ ቅዱሳን እንደኖረች #ተአምረ #ማርያም ሲገልጽ <<ልጃቸውን #ማርያምን #በንጽህና ሲያሳድጉ 3 ዓመት በተፈጸመ ጊዜ #ሐና ባሏን #ኢያቄምን ወንድሜ ሆይ ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር #ብጽአት አድርገን እንስጥ #ልጃችን ቤተ #እግዚአብሔርን #እንድታገለግል ነው እንጂ በዚህ #ዓለም እኛን ልታገለግል እንዳልተሳልን አስብ አለችው። #ኢያቄምም ይህን ነገር ከሚስቱ #ሐና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው። ለመንገድ የሚሆነውን #ስንቅና ለቤተ #እግዚአብሔር የሚሆነውንም #መባዕ ሁሉ አዘጋጅ። #ቤተሰቦቻቸውንና #ባልንጀሮቻቸውን #ዘመዶቻቸውንም ሁሉ ጠራ። ልጃቸውንም ይዘው ሄደው ወደ #ቤተ መቅደስ አስገቧት። ካህናት #በቤተ #መቅደስም ያሉ ሁሉ በሰሙ ጊዜ እነሱም ለመቀበል ወጥተው መንፈሳዊ #ሰላምታ ሰጡአቸው። #ኢያቄምና ሚስቱን #ሐናን ልጃቸውንም #ማርያምን አመሰግነዋቸው #በአንብሮተ-እድ (እጅ በመጫን) ፈጽመው ባረኳቸው። እግዚአብሔርም ሃዘናችሁን #በእውነት ተቀብሏችኋል። #ቸር በምትሆን በዚች ልጅም ደስ አሰኝቷችኋል አሏቸው። #እመቤታችንም ለእግዚአብሄር #ለእናትነት የተመረጥሽ #ንዑድ #ክብርት ሆይ #ፍቅር ይገባሻል አሏት። ታቅፈው ይዘው #በታህሳስ 3 ቀን #በእግዚአብሄር #ፍቅር ወደ #ቤተ መቅደስ አስገቧት[1]>>።

▶️ ቅዳሴ ማርያም ንባቡና አንድምታው እንዲሁም #የወንጌል አንድምታው <<ካህናቱ ወደ #ቤተ #መቅደስ (ቅድስተ ቅዱሳን) ከማስገባታቸው በፊት #የምግቧ ነገር እንዳሳሰባቸው ይገልጽና #ፋኑኤል የሚባል #መልአክ #ሰማያዊ #መጠጥና #ምግብን አምጥቶ ለብቻዋ ሲመግባት አይተው <<የምግቧስ ነገር ከተያዘልን #ከሰው ጋር ምን ያጋፋታል>> ብለው #ከቤተ መቅደስ (ቅድስተ ቅዱሳን) ውስጥ አስገብተዋት 12 #ዓመት በዚያ ውስጥ #እንደኖረች ይገልጻሉ[2]።
<<እርሷም #ከቤተ መቅደስ (ቅድስተ-ቅዱሳን) ውስጥ #በመንፈስ ቅዱስ ሞግዚትነት ገብታ ወንበሯን ዘርግታ #ከደናግለ እስራኤል የተካፈለችውን #ወርቅና #ሐር እያስማማች ስትፈትል #በአምሳለ አረጋዊ (በሽማግሌ) መልክ ገብርኤል መልአክ መጥቶ ትጸንሻለሽ ብሎ እንዳበሰራት የቅዳሴ ማርያም አንድምታው ይነግረናል[3]። እንዲሁም በቤተክርስቲያኗ #ትውፊትና #ትምህርት መሰረት ከማርያም ጀርባ #መንጦላኢተ - ቤተመቅደስ (የቤተመቅደስ መጋረጃ) እና ከፊት ለፊቷ #የቅዱሳት መጽሐፍት ማንበቢያ #አትሮንስ (Pulpit) የሚታየውና መልአኩ #ገብርኤል በብርሃን ተከቦ #ሲያበስራት የሚያሳየው #ስዕል እርሷ #በቤተመቅደስ ውስጥ እንደኖረችና በዚያ ውስጥ #ክርስቶስን የምትወልድ መሆኗን የተበሰረችበት መሆኑን የሚገልጽ #ስዕል ነው።

ይህንንም #ታሪክ መሠረት ተደርጎ <<ዘነበርኪ ውስተ ቤተ መቅደስ ከመታቦት ዘግንቡር እምዕፅ ዘኢይነቅዝ፤ ሥርግው በወርቅ ንጡፍ ወልቡጥ በዕንቁ ባሕርይ ዘየኅቱ ዘብዙኅ ሤጡ ከመዝ ነበርኪ ውስተ #ቤተ መቅደስ - አምላክን የወለደሽ እመቤታችን #ድንግል ማርያም ሆይ #ከማይነቅዝ #እንጨት #የተቀረጸ ዋጋው እጅግ ብዙ የሆነና በከበረ #ወርቅ እንደተለበጠና እንዳማረ #ታቦት #በቤተ መቅደስ ኖርሽ>> እየተባለ ይዜማል[4]።

▶️ እንዲሁም <<አማናዊት #ታቦት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም[5] #ንጽሕተ ንጹሐን #ቅድስተ ቅዱሳን በመሆኗ #በንጽሕና #በድንግልና ጸንታ #በቤተመቅደስ ኖራለች>> ተብሎአል[6]። እንዲሁም #ቤተመቅደስ መኖሯም #በማህሌተ ጽጌ መጽሐፍ #በግጥምና #በዜማ <<የኅዝነኒ ማርያም ዘረከበኪ ድክመትና አመ ቤተመቅደስ ቦእኪ እንዝትጠብዊ ሐሊበ ሐና ወያስተፌሥሐኒ ካዕብ ትእምርተ ልሕቀትኪ በቅድስና ምስለ አብያጽሁ ከመአብ እንዘ ይሴሲየኪ መና ፋኑኤል ጽጌነድ ዘይከይድ ደመና - ማርያም የሃናን ወተት እየጠባሽ ወደ #ቤተመቅደስ በገባሽ ጊዜ ያገኘሽ #ድህነት (ብቸኝነት) ያሳዝነኛል፡ ዳግመኛም በደመና የሚመላለስ #ደመናን የሚረግጥ #የእሳት አበባ #ፋኑኤል ከጓደኞቹ #መላእክት ጋር መናን የመገበሽ #በንጽሕና የማደግሽ #ተአምር ደስ ያሰኛል[7]>> ይላል።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
________
[1] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ "ተአምረ ማርያም" 2፤ 27-30፤ 3ኛ ዕትም፤ ገጽ 18፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1989 ዓ.ም።

[2] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ "ቅዳሴ ማርያም" ንባቡና አንድምታው 5፥15፣ 44 ገጽ 120፣ 123. ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1983 ዓ.ም።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ ወንጌል ቅዱስ ንባቡና አንድምታው፤ የሉቃስ ወንጌል 1፥27፥ ማብራሪያ ገጽ 265፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1997 ዓ.ም።

[3] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ "ቅዳሴ ማርያም" ንባቡና አንድምታው 5፥44 ገጽ 125፣ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1983 ዓ.ም።

📚፤ አንቀጸ ብርሃን ትርጓሜው፤ ገጽ 411።

📚፤ አንዱአለም ዳግማዊ (መምህር)፤ "ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት"፤ ብራና ማተሚያ ድርጅት፤ አ.አ፥ ገጽ 178።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ "ተአምረ ኢየሱስ" 3ኛ ተአምር ቁ.2፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ ገጽ 14፤ 1994 ዓ.ም።

[4] 📚፤ አንቀጸ ብርሃን ትርጓሜው፤ ገጽ 404።

📚፤ አንዱአለም ዳግማዊ (መምህር)፤ "ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት"፥ ገጽ 276 ብራና ማተሚያ ድርጅት፤ አ.አ፥ ሚያዚያ 1998 ዓ.ም።

[5] 📚፤ አግዛቸው ተፈራ (ዲያቆን)፤ "አልተሳሳትንምን?" 2ተኛ ዕትም፤ ገጽ 85፤ ሶላር ማተሚያ ቤት፥ መስከረም፤ 2010 ዓ.ም፤ አ.አ ኢትዮጵያ።

[6] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ "መጽሐፈ ሰዓታት" ገጽ 148።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ መጽሐፈ ቅዳሴ ንባቡና ትርጓሜው፤ ገጽ 169፥ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ 1983 ዓ.ም።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ ውዳሴ ማርያም ንባቡና ትርጓሜው፤ ገጽ 194፤ ትንሣኤ ዘጉባኤ አዲስ አበባ፤ 1983 ዓ.ም።

[7] 📚፤ አስረዳ ባያብል (ሊቀ ጠበብት)፤ "ማህሌተ ጽጌ ትርጓሜ፤ አ.አ፥ ገጽ 79፥ 1998 ዓ.ም።

(7.2▶️) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat
▶️ ወደ #ቅድስተ #ቅዱሳኑ (ቤተ መቅደሱ) ውስጠኛ #ክፍል ለአገልግሎቱ የሚገባው #ሊቀ ካህኑ ብቻ ሆኖ #በአመት 1 ቀን እርሱም #በማስተሰርያ ቀን #ስለራሱና #ስለህዝቡ #መስዋዕትን ይዞ #በእግዚአብሄር ፊት ይቆማል {ዘጸ 28}። #የሊቀ ካህኑ ልብሰ #ተክህኖ #በ4 #ቀለማት ማለትም #ከነጭ#ከሰማያዊ#ከሐምራዊና #ከቀይ #በፍታ #በወርቅ የተለጠፈ ነበር {ዘጸ 28}። የላይኛው አላባሽ #ኤፉድ ሲባል {ዘጸ 39፥2} #በቀኝና #በግራ ትከሻው ላይ ሁለት የመረግድ #ድንጋዮች ነበሩት። በእነዚህ #ሁለት የከበሩ #ድንጋዮች በእያንዳንዱ ላይ #የ6 ነገድ #ስም በሁለቱም ላይ #የ12ቱ ነገደ #እስራኤል ስም #ተቀርጾባቸዋል {ዘጸ 28፥9 እና 12}። በእነርሱም አማካኝነት #ሊቀ ካህኑ #የህዝቡን #ስም በአጠቃላይ በትከሻው ይሸከማል። #የደረት ኪሱ #አራት ማዕዘን ያለው ሆኖ #በወርቅ ጥልፍ የተሰራ #የ12 ነገድ #ስም የተቀረጸባቸው #የሚያንጸባርቁ #የከበሩ #ድንጋዮች እንደ #ፈርጥ ሆነው የተሰሩ ናቸው {ዘጸ 28፥29}። #የደረት ኪሱ ታጥፎ የተደረበ ነው በውስጣቸው #ኡሪምና #ቱሚም ይይዛሉ {ዘጸ 28፥30}። #ቀሚሱ ሙሉ በሙሉ #ሰማያዊ ሲሆን በታችኛውም ዘርፍ ዙሪያ #በ3 #ቀለም የተሰራ #የሮማን ፍሬ #ቅርጽ #ከወርቅ #ሻኩራ ጋር ተሰባጥሮ ይደረግበታል። የሻኩራዎቹ #ድምጽ #ለቀሚሱ ውበትን ይሰጠዋል። #ጥምጥሙ ደግሞ #ካህኑ በራሱ ላይ የሚጠመጥመው ሲሆን ከጥሩ #በፍታ የተሰራ ነው <<ቅድስና ለእግዚአብሔር>> የሚል ጽሑፍ #ከወርቅ በተሰራ #ዝርግ #ጌጥ ላይ ተቀርጾ በዚህ #ጥምጥም ላይ #ይንጠለጠልበታል {ዘጸ 28፥36}።
▶️ ይህም #ቤተመቅደስ #ማርያም በነበረችበት #ዘመን የነበረ ሲሆን ሁሉም #ሴቶች #በቁ.4 ላይ በተገለጸው ውስጥ በፍጹም #አይገቡም ነበር። ይሁን እንጂ #በውጭ (በተራ ቁ.7 ላይ) በተገለጸው #አደባባይ ላይ እንደ #የ91 ዓመቷ ዕድሜ #የፋኑኤል ልጅ #ሃና #ነብይት ዓይነቶች {ሉቃ 2፤ 36-38} #መቆም ይችሉ ነበር።

እስከዛሬም ድረስ የትኛዋም #ሴት ብትሆን #ቤተመቅደስ (ቅድስተ ቅዱሳን) ውስጥ #መግባት አልቻለችም። #ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን #ሴቶች ወደ #ቤተ መቅደስ እንዲገቡና #በመቅደስ ውስጥ #እንዲጸልዩ ለአፍታ እንኳ አለመፍቀዷ የራሷ #ስርዓት #ይደነግጋል[1]።
ታድያ #ማርያም በየትኛው #ቦታ በየትኛው #ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ #መኖሪያዋ አድርጋ አደገች? አዎን #ማርያም #ቤተ መቅደስ ነበረች የሚለው #ሃሳብ ከየት መጣ ቢባል #ከቁርዓን ነው {ሱረቱ አልዒምራን 3፥37}። እርሱም #ስለቤተ መቅደሱ ሁኔታ #እውቀት የለውምና አይፈረድበትም።
ይህን ያዩ ሌሎች #ሴቶች በዚህ ወራት አምላክ #ከድንግል #ይወለዳል የተባለው ከአንቺ ይሆንን? ብለው ዘበቱባት። ወዲያው #መልአኩ መጥቶ #ትጸንሲ (ትጸንሻለሽ) አላት ዝም ብላ ሄደች። ከቤትም ደርሳ ውሃውን ስታወርድ #ትጸንሲ (ትጸንሻለሽ) አላት ይህ ነገር ደጋገመኝ #ከቤተመቅደስ ሄጄ ልረዳው ብላ #ከደናግለ #እስራኤል ጋር ተካፍላ እያስማማች የምትፈትለው #ሐርና #ወርቅ ነበር። ያንን ይዛ ሄደች #ከቤተ #መቅደስ ተቀምጣ #ሐርና #ወርቁን እያስማማች ስትፈትል #መልአክ መጥቶ #ትጸንሲ (ትጸንሻለሽ) አላት እፎኑ ይከውነኒ ዝንቱ እንዝ ኢያአምር ብእሴ - #ወንድ #ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆንልኛል? አለች። እኔ ይህን አላደርገውም #እንደምን #ይሆናል ስትለው ነው ከዚህ ቡኋላ መንፈሰ እግዚአብሔር ቅዱስ ይመጽእ ላእሌኪ - ቅዱስ #የእግዚአብሔር #መንፈስ #በአንቺ ላይ #ይመጣል አላት። ይኮነኒ በከመ ትቤለኒ (እንደ ቃልህ ይሁንልኝ) አለችው። ይህን #ቃሏን ምክንያት አድርጎ #በማህጸኗ ተቀርጾአል[4]>> ብለው ያቀርባሉ።

▶️ የዚህ #ተረት #ፈጣሪ #በመጽሐፍ ቅዱስ #በዮሴፍ ቤት #ናዝሬት #ከተማ ነበረች የሚለውን #የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ #ገለጻ በመተው ሌላ #ያልነበረና የሌለ #ታሪክ ጽፏል። ይህ ደግሞ በቃሉ ላይ #አመጽና #መሸቃቀጥን ያመለክታል። አዎን ቅዱስ #ገብርኤል #ማርያምን ሲያበስራት #በእጮኛዋ #ዮሴፍ ቤት #በናዝሬት ከተማ ነበረች እንጂ #ቤተ መቅደስ ወይም #በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ አልነበረችም #ወቅቱና #ሁኔታውም አይፈቅድም {ሉቃ 1፥26}።

▶️ አንዳንዶችም #በቤተ መቅደስ ነበረች የሚለውን #አባባል #መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም ብለው #በመቃወም #ማርያም የነበረችው #በቤተ መቅደስ #ቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ሳይሆን #በቤተ መቅደሱ ግቢ #በማህደረ #ደናግል ውስጥ ትኖር ነበር የሚሉ አሉ። ነገር ግን #ሄሮድስ በሰራው #ቤተ መቅደስ #አደባባይ ጊቢ ውስጥ ይኖሩና ቆመው #ለአፍታ ያህል ይጸልዩ የነበሩት #አሮጊቶችና #መበለቶች እንደነ #ሃና #የሳሙኤል እናት {1ኛ ሳሙ 1፥9 እና አሮጊቷ ሃና} ሉቃ 2፤ 36-38} እንጂ #ደናግል ወጣት #ሴቶች በጭራሽ አይገቡምና ይህም #ጥናቱ ያላላቀ #ጅምር #አንካሳ #ሃሳብ ነው።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ ፍትህ መንፈሳዊ አንቀጽ 1 ዲድስቅሊያ 44።

📚፤ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ፤ <ስርዓተ ቤተ ክርስቲያን 3ኛ ዕትም፡ ብራና ማተሚያ ድርጅት፤ አ.አ፥ ገጽ 18፡ 1995 ዓ.ም።

📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፡ "ፍትሐ ነገስት ንባቡና ትርጓሜ፤ አንቀጽ 1፤ 13፡ ገጽ 23፤ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፡ አ.አ፡ 1990 ዓ.ም።

[2] 📚፤ ኢንተርናሽናል መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፤ መጽሐፍ ቅዱስ አዲሱ መደበኛ ትርጉም፤ የሉቃስ 2፥4 እና 22 ማብራርያ፡ ገጽ 1531-1532፡ 1993 ዓ.ም።

[3] 📚፤ አባ ቤተማሪያም እና መዘምራን ሞገስ ዕቁባ ጊዮርጊስ፤ "አምስቱ አዕማደ ምሥጢር ምስል ሥነፍጥረት አንድምታ"፤ አክሱም ማተሚያ ቤት፤ አክሱም፡ ገጽ 36፤ 1991 ዓ.ም።

📚፤ አስረዳ ባያብል (ሊቀ ጠበብት)፤ "ማህሌተ ጽጌ ትርጓሜ"፤ አ.አ፡ ገጽ 80፤ 1998 ዓ.ም።

[4] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ "ውዳሴ ማርያም ንባቡና አንድምታው" ዘሰንበተ ክርስቲያን፤ ገጽ 210፥ ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1983 ዓ.ም።

(7.4▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat