ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ #ብዙ ሴቶች #ማርያም በሚል ስም ይጠራሉ[1]። [ለምሳሌ]👇 〽️ 1፦ "የሙሴ እህት ማርያም" /ዘጸ 2፥4-8/ ▶️ የዚችን #ማርያም ታሪክ #በመጽሀፍቅዱስ ውስጥ ስናይ #ወንድሟ #ሙሴ በወንዝ #ዳር #በተጣለ ጊዜ በእርሱ ላይ የሚሆነውን #ለማወቅ ስትመለከት ወደ ወንዙ የመጣችውን #የፈርኦንን #ልጅ #በጥበብ አነጋግራና #እንድታጠባው የገዛ #እናታቸውን #በሞግዚትነት ስም አገናኝታ…
▶️ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ለ"ማርያም" ለሚለው ስም የተሰጡ #ትርጉሞች #የቤተስክርስቲያን #አባቶችም ሆኑ #ወጣት #ሰባኪያንና #ህዝቡም በብዛት የሚያውቁት #የተለመደ #ትርጉም ነው። የሚገርመው ደሞ #የስሙ #ትርጉሞች ብዙ #ማርያም የተባሉ #ሴቶች እያሉ ማእከል ያደረገው ግን #የጌታችን #እናት #ድንግል #ማርያምን ብቻ ይመስላል። እነዚን #ትርጉሞች ይዘን ለሌሎች < #ማርያም> ለተባሉ #ሴቶች ትርጉሙን ብንሰጣቸው #የትርጉሙ #ባለቤቶች ራሱ #ይሸማቀቁበታል። [ለምሳሌ]፦
#በስም #ደረጃ ከክርስቶስ እናት ጋር #ምንም #ልዩነት ላልነበራት #ለመግደላዊት #ማርያም ትርጓሜውን ብንሰጣት
< #ማርያም> ማለት < #ፍጽምት ማለት ነው>። #መልክ #ከደም #ግባት አስተባብራ ተገኝታለችና ፍጻሜው ግን #ንጽሐ ሥጋ #ንጽሐ ነፍስ #በድንጋሌ ሥጋ #በድንጋሌ ነፍስ አስተባብራ ተገኝታለችንና ብንል #በወንጌል እንደተገለጸው #መግደላዊት #ማርያም #ድንግል አልነበረችም።

▶️ ሌላውንም #ትርጉም ብናይ (ጸጋ ወሀብት) ለሰው ሁሉ #ጸጋ ሆና #ተሰታለችና#የመንግስተ #ሰማይም #መሪ ናት፤ " #ከፈጣሪ በታች #ከፍጡራን በላይም ነች"፤ #ለሰውና #ለእግዚአብሄር #ተላኪ ናት ብንል፤ ምኗ #ለሰው #ሁሉ #ጸጋ ሆኖ #እንደተሰጠ፣ ማንንስ #መንግስተ #ሰማይ #መርታ እንዳስገባች፣ #ከፍጡራን በላይ ያደረጋትስ ምንድነው ብንል #ሊቃውንት ነን የሚሉ ሰዎች #የተምታታና #የተጋጨ ወይም #የእፍረት መልስ ካልሆነ በቀር #መልስና #ማስረጃ የሌለው ነገር ነው። በመሆኑም ከላይ እንደተጠቀሰውም " #ማርያም" የሚለውን #የስም ትርጉም ለሌሎች " #ማርያም" ለተባሉ ሴቶች #ትርጉሙን ብንሰጠው #የማያስኬድና #ስህተት ሆኖ እናገኘዋለን።

️የስም #ለውጥ ባይኖረውም ብቻ #ትርጉሙ የሚሰራው ለጌታችን እናት #ለድንግል #ማርያም ብቻ ነው #ብንል #እንኳን
" ማርያም << #ፍጽምት በስጋም በነፍስም ነች>> ማለት #ጻድቅ #የለም አንድስኳ {ሮሜ 3፥11} ከተባለው እና ከሌሎች #የመጽሀፍቅዱስ ክፍሎች ጋር የሚቃረን ይሆናል።
በምድር ላይ #ኃጢአትን አላደረኩም፤ #የውርስ #ኃጢአት የለብኝም የሚል #ፍጹም ወይም #ፍጽምት ቢገኝ ኖሮ #ክርስቶስ ራሱ #መምጣት ባላስፈለገው ነበር።

▶️ ሁለተኛውን ትርጉም ደሞ ብናይ #ጸጋና #ሀብት ሆኖ #ለምድር የተሰጠው፤ የተዘጋውንም #የገነትን #ደጅ #በከበረ ሞቱ ከፍቶ #ከተሰቀለው #ወንበዴ አንዱን እንኳ #እየመራ #መንግስተ #ሰማያት ያስገባ፤ #በእግዚአብሄርና #በሰው መካከል ሆኖ #የመካከለኛ አገልግሎት #የሰጠውና #የሚሰጠው ጌታችን መድሃኒታችን #ኢየሱስ እንጅ ሌላ #ማንም አይደለም። ለዚህም እባክዎትን #መጽሀፍ #ቅዱስዎትን ገልጠው እነዚህን #የተጠቀሱ ጥቅሶችን ያንብቡ። {ቲቶ 2፥11-14፣ ኤፌ 2፥8፣ ሮሜ 5፥17፣ ዩሐ 3፥16፣ ሉቃ 23፤ 42-43፣ 1ጢሞ 2፥5፣ ዕብ 7፥24}።

▶️ ሌሎች #ሊቃውንትና #ተርጓሚዎችም << ማርያም ማለት በዚህ ዓለም #ከሚመገቡት ሁሉ #ምግብ #ለአፍ የሚጥም #ለልብ የሚመጥን < #ማር> ነው፤ #በገነትም #በህይወት ለተዘጋጁ #ጻድቃንና #ቅዱሳን < #ያም> የሚባል #ምግብ አላቸው፤ ስለዚህ ሁለቱን < #ማር" እና #ያም> የተባሉትን #ሁለት ፊደላት ስናገጣጥማቸው #ማርያም የሚል ስም #ተገኝቷል ምክንያቱም #እናትና #አባቷ አንቺ ከዚህም ኩሉ #የበለጥሽ #ጣፋጭ #የከበርሽ ነሽ ሲሉ #ማርያም ብለዋታል>> ይላሉ።

▶️ አሁንም ሌላ #ትርጉማቸውን ይቀጥሉና " #ማርያም ማለት #ሠረገላ #ፀሐይ ማለት ነው፤ #መንግስተ #ሰማያት ታገባለችና ፤ አንድም #ማርያም ማለት #ውኅብት #ወስጥወት (የተሰጠች) ማለት ነው፤ እመቤታችን እግዚእትነ ማርያም የተወለደች ዕለት በአባት እናቷ ቤት ውኅብት ወስጥወት ሆና ተገኝታለች፤ ኋላም በዓለሙ ሁሉ #አማላጅ ሆና #ሞታለችና ስለዚህ ውኅብት ወስጥወት (የተሰጠች) ናት" ይላሉ[3]።

️አሁንም እነዚህ #ሁለት #ትርጉሞች የአንድ ሰውን #የጌታችን የመድሃኒታችን #የኢየሱስ #ክርስቶስን #እናት #ድንግል #ማርያምን #ማእከል ያደረገ እንጅ ሌሎቹን #የማርያምን #ስም የያዙትን #ሴቶች ያገናዘበ አይደለም። ሆኖም ግን #የአማርኛውን ፊደል ወይም #ሐረግ ብቻ ተከትሎ < #ማር> እና < #ያም> በሚል የተከፋፈለ #ትርጉም መስጠት #አዋጭነት የለውም። ምክንያቱም ስያሜው #የእብራይስጥ #ቋንቋ እንጅ #የአማርኛ ወይም #የግእዝ አይደለም። እንደዛም እንኳን ቢሆንና ብንወስደው < #ያም> የሚባል #ቅዱሳኑ የሚበሉት #ምግብ አለ" ስለተባለው ሁኔታ #መጽሀፍ #ቅዱስም ሆነ ሌሎች መጽሀፍት #በሰማይ #ምግብ እንዳለ አይናገሩም። እንደውም #መጽሀፍ ቅዱስ #እግዚአብሔር #ምግቦችን ሁሉ #በምድር እንዳደረገ ነው የሚናገረው። {ዘፍ 1፤29-31} በተጨማሪም #የእግዚአብሔር ቃል << #መብል #ለሆድ ነው #ሆድም #ለመብል ነው እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንንም #ያጠፋቸዋል>> ይላል {1ቆሮ 6-13}።
በመሆኑም #መብል የእግዚአብሔር ዘላለማዊ #እቅዱ ስላልሆነ #በመንግስተ #ሰማያት አስቤዛ መግዛት መለዋወጥ ምግብ ማብሰል ... የለም፤ #አይኖርምም#አልተጻፈምም። በመሆኑም < #ማር" እና " #ያም> ብሎ ከፋፍሎ #የስም #ትርጉም መስጠቱ #ትርጉም የለሽ ይሆናል።

▶️ ሌላው << #ለዓለሙ ሁሉ #አማላጅ ሆና #ሞታለችና #ማርያም ማለት #ስጦታ ማለት ነው>> ብሎ መናገርና መጻፍ #ስለበደላችንና #ስለሐጢአታችን #በቀራኒዮ #መስቀል አደባባይ ላይ #የሞተውን ለይቶ #አለማወቅ ወይም #ክህደት ነው። #ለዓለም ሁሉ #ኃጢአት #አስታራቂ እንዲሆን የተሰጠንና ከአባቱም ጋር #ያስታረቀን ስለበደላችን #የሞተልን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ብቻና ደግሜ እላለሁ #ብቻ ነው። {1ጢሞ 1፥15፣ ሮሜ 3፥23፣ ሮሜ 5፥8፣ ሮሜ 8፥34፣ ዕብ 7፥24}።
▶️ ማርያም #ስለመሲሁ የመምጣት #ተስፋ ብታውቅም እንዴት #እንደሚፈጸም ግን አታውቅም ነበር። #በሉቃ 1፥34 ላይ #አለማመኗን የሚያሳይ ሳይሆን #እምነቷን የሚገልጽ ነበር። አንዲት #ልጃገረድ እንዴት #ከወንድ ጋር #ሳትገናኝ #ልትወልድ ትችላለች ብላ በማሰቧ #እጮኛዋ ከሆነው #ከዮሴፍ ጋር #ባለመጋባቷና #ግንኙነት ፈጽማ ባለማወቋ #መልአኩን <<ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?>> ብላ ጠየቀችው። #መልአኩም ይህ #በመንፈስቅዱስ የሚፈጸም #ተአምር እንደሆነ ነገራት። ደግሞም #ከአዳም #የውርስ ኃጥያት #በመንፈስቅዱስ መጸለል(መጋረድ) ምክንያት የሚወለደው #ህጻን <ቅዱስ> እንደሚሆን አመለከታት።

▶️ መልአኩ #መልእክቱን የደመደመው ለማርያም #የማጽናኛ #ቃል በመስጠት ነበር። ይኸውም #በዕድሜ የገፋችው ዘመዷ #ኤልሳቤጥ #ወንድ ልጅ #መጸነሷና 6ኛ ወሯ መሆኑን በመግለጽ #ለእግዚአብሄር #የሚሳነው ነገር የለምና አንቺም #መጸነስ ትችያለሽ በማለት #አስረዳት

▶️ ከዚህ ቡኋላ #ማርያም እንደታዛዥ #ባርያ ራሷን #ለእግዚአብሄር #በመስጠት <<እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ>> በማለት #የእምነት #ምላሽ ሰጠች {ሉቃ 1፥38}። መልአኩም ይህን #ውይይት እንደጨረሰ ከእርሷ ተለይቶ #ሄ

▶️ እንግዲህ በዚህ #ውይይት ውስጥ እጅግ #ዝቅተኛ #የኑሮ #ደረጃ ውስጥ ትኖር የነበረች #ልጃገረድ #የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመፈጸም #ለጌታ ሙሉ በሙሉ ራሷን #መስጠቷን ስናይ እንዴት የሚገርም ነው ያሰኛል። #ማርያም በእርግጥም #ለእግዚአብሄር #የተሰጠች #ሴት ነበረች። ይሁን እንጂ በአሁኑ #ዘመን በዚህ 'በቅድስት ድንግል #ማርያምና በቅዱስ #ገብርኤል' መካከል የተደረገውን #ውይይት ከተጻፈው #ውጪ በርካታ #የሃይማኖት መጽሐፍት በተለይም #አዋልድ መጽሐፍት #ኢ-መጽሀፍ ቅዱሳዊ ጽንፈኛ #አስተምህሮቶችን ለብዙ ዓመታት #ሲያንጸባርቁ ቆይተዋል። ከዚህም የተነሳ ማርያምን የሃይማኖታቸው ማዕከል ያደረጉ በርካታ መናፍቃን ስለመነሳታቸው ታሪክ ይዘግባል።

👉 ለምሳሌ #የዘውትር ጸሎት መጽሐፍ የሆነው <<ይወድስዋ መላዕክት - መላዕክት ማርያምን ያመሰግኗታል>> በሚለው አርስቱ <<መልአኩ ገብርኤል ማርያምን •ድንግል ለአንቺ ክብር ምስጋና ይገባሻል• አላት፣ •ወላዲት አምላክ ምስጋና ይገባሻል•፣ •ቅድስት ነሽና ምስጋና ይገባሻል•፣ •የመለኮት ማደሪያ ነሽና ምስጋና ይገባሻል•፣ •የተሸለመች ድንኳን ነሽና ምስጋና ይገባሻል•፣ •የሁሉ እመቤት ማርያም ምስጋና ይገባሻል•፣ •የሁሉ ፍቅረኛ ማርያም ምስጋና ይገባሻል•፣ •ልዑል ማደሪያው ትሆኚ ዘንድ መርጦሻልና ምስጋና ይባገሻል•፣ •በወርቅ የተሸለምሽ የርግብ ክንፍ በብር ያጌጥሽ ምስጋና ይገባሻል•፣ •ጎኖችሽ በወርቅ አመልማሎ የተሸለሙ ለአንቺ ምስጋና ይገባሻል•፣ •ከጸሀይ 7 እጅ የምታበሪ ክብርሽ ከአድባራቱ ሁሉ ከፍ ከፍ ያለ ለአንቺ ምስጋና ይገባሻል•[3]>> ይላል። ይህ #ጸሎት በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ #በቃል አልያም #በንባብ ዘውትር ወደ #ማርያም የሚቀርብ #ምስጋና ነው።

▶️ ይሁን እንጂ #ቆም ብለን በእውኑ ከላይ የተገለጸውን #ንባብ (አንቀጽ) #ቅዱስ ገብርኤል የተናገረው ነውን? #መላእክትስ ማርያምን #ያመሰግኗታልን? እኛስ እንዲህ ያለውን አንቀጽ አስቀምጠን ወደ #ማርያም #እንድንጸልይ (እንድናመሰግን) #ሕግ ተሰጥቶአልና? ብለን ብንጠይቅና ለማየት ብንሞክር ፈጽሞ የሌለና #ያልተባለ ወደፊትም #የማይባል እንደውም #ኃጢአት እንደሆነ #መጽሐፍ ቅዱሳችን በግልጽ ይናገራል።

▶️ በመሆኑም #መላእክት #የሚያመሰግኑትንና #ምስጋና #የሚገባውን ጠንቅቀው ስለሚያቁ ሲያመሰግኑ እንዲህ ይላሉ፦

<<በታላቅም ድምፅ። የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ።. . . በረከትና ክብር ምስጋናም ኃይልም ከዘላለም እስከ ዘላለም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው፥ ለበጉም ይሁን. . . በረከትና ክብር ጥበብም ምስጋናም ውዳሴም ኃይልም ብርታትም ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤ አሜን አሉ።>>

የሚል ክርስቶስን ማዕከል ያደረገ አምልኮና ምስጋና ብቻ ነው {ራዕ 5፤10፣ 12-13;፣ ራዕ 7፥12፣ በተጨማሪም ራዕ 4፥8፣ 11፥15፣ 12፥10፣ 15፥3፣ 19፥1. . .።}

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ የኢ.ኦ.ተ.ቤ/ክ፤ ወንጌል ቅዱስ፡ ሉቃስ አንድምታ 1፥47፣ ገጽ 268። ትንሳኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት፤ አ.አ፤ 1997 ዓ.ም።

[2] የእግዚአብሄርም ቃል <<ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤ እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ፥>> {1ኛ ቆሮ 1፤ 27-28} የሚለው ለዚሁ አይደል??

[3] የዘውትር ጸሎት መጽሐፍ <ይወድስዋ መላእክት> ቁ.3።


(4.1▶️ጥያቄ) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat