ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
2.83K subscribers
536 photos
68 videos
81 files
391 links
〽️ ገድላትና ድርሳናት
〽️ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ
〽️ አዋልድ መጻሕፍት
〽️ ሌሎችንም ያለቦታቸው የገቡ የመጽሐፍቅዱስ ጥቅሶችና ኢ-መፅሐፍቅዱሳዊ የሆኑ ትምህርቶቻቸው በመፅሐፍ ቅዱስ ሲመዘኑ

እውነትን ታውቃላቹ እውነትም አርነት ያወጣቹሀል [ዮሐንስ 8፥32]
@teedy
@teedy

ኢየሱስ ማነው?👇
@Who_is_jesus
Download Telegram
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽 #ኢየሱስ #አማላጅ መሆኑን መቀበል የከበዳቸው ሰዎች፤ ክፍሉ(ሮሜ 8፥34) ምን ያህል #እንዳስጨነቃቸው የሚያሳየው ለአንዱ #ጥቅስ የሚሰጡት የመከላከያ #ሐሳብ #ብዛት ነው፡፡ ቀደም ሲል ከቀረቡት #ሐሳቦች #ሌላ ደግሞ፤ መምህር በርሀ ተስፋ መስቀል እንዲህ ይላሉ.. 〽️ 3፦ ‹‹ስለ እኛ #የሚማለደው ተብሎ መጻፍ ሲገባው ‹ #ለ› ን ‹ #ል› በማድረግ ስለ እኛ #የሚማልደው ተብሎ…
🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽🔽

እንደገና ከላይ ከቀረቡት #ሐሳብ የተለየ ደግሞ መሪጌታ ሀየሎም በርሄ እንዲህ በማለት ያስቀምጣሉ...

〽️ 4፦ ‹‹ይህ ሕያው #ሥጋውና #ደሙ ሁል ጊዜ #ሰውን ወደ #እግዚአብሔር #ሲያቀርብ የሚኖር ከእግዚአብሔርም ጋር የመታረቂያው #ብቸኛ #መንገድ በመሆኑ #አማለደን /አስታረቀን/ ሲል ገልጦታል›› የሚል ሐሳብ አቅርበዋል፡፡
📖/፤ ኃየሎም በርሄ (መሪጌታ)፣ ሁለቱ ኪዳናት (ዐዲስ አበባ 2002) ገጽ 219።

▶️ እኚህ ጸሀፊ ደግሞ ከላይ የቀረቡትን ሐሳቦች በሙሉ ተቃርነው፤ ይልቁንም አዎ #ኢየሱስ ይማልዳል! ነገር ግን #የሚያማልደው #በቅዱስ #ቁርባን ነው ይሉናል፡፡ እንግዲህ ማንኛውም #ልባም #አንባቢ ክፍሉን ተመልክቶ #መረዳት #እንደሚችለው በዚህ #ምንባብ ውስጥ #ከክርስቶስ #ሥጋና #ደም (ከቅዱስ ቁርባን) ጋር የተያያዘ #ሐሳብ ማግኘት ፈጽሞ አይችልም፡፡ ይህን #ምንባብ #መሠረት አድርጎ ስለ #ቅዱስ #ቁርባን #ለማስተማር የሚሞክር #ሰው ሆነ ብሎ የሰዎችን #ትኵረት ወደ ሌላ #አቅጣጫ #ለመውሰድ ያሰበ #ሰው እንጂ #ጥቅሱን መሠረት አድርጎ ማብራሪያ #እየሰጠ አለመሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
እነዚህ ሁሉም እንግዲህ #መምህራን ተብለው መድረክ ላይ የሚቆሙና ይህን እና ይህን መሰል #የኑፋቄ ትምህርት #በህዝቡ ላይ የሚረጩ፤ #ከእግዚአብሄር ቃል ይልቅ ለፈቃዳቸውና ላሉበት ባህላዊ እምነት ቅድሚያ የሚሰጡ ሰዎች ናቸው። እንዳያችሁት #አንድ #ጥቅስ ላይ ራሱ እንዲህ ያለ #አለመግባባት ይታይባቸዋል፡፡ እርስ በእርስ ያልተስማሙ ሰዎች ታዲያ እንዴት ነው #ከቅዱሱ #መጽሐፍ ጋር ተስማምተው #ለማስተማር የሚችሉት? ስለዚህም እኛን ለማስተማር ከመሞከራቸው በፊት #እርስ በእርሳቸው #ይስማሙ ዘንድ ይሄው ወንድማዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ይህ ሁሉ ግን ለምን ይሆን? ስንል ምክንያቱም #ቤተ ክርስቲያኒቱ #ከክርስቶስ #የማዳን ሥራ ጋር የተሳሰረውን #የምልጃ ስራውን አልቀበልም በማለቷ ነው፡፡

@gedlatnadersanat @teeod
ገድላትና ድርሳናት በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘኑ
▶️ እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉት #ሀሳቦች በሙሉ #የተፈለሰፉት #ማርያም <<ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች>> እንደሆነች #መጽሀፍ ቅዱስ እንደሚናገር በማሰብ ሲሆን ከላይ እንደተገለጸው #ከእግዚአብሄር #ቀጥላ #ሁለተኛ #አምልኮት የሚቀርብላት ሆናለች። ነገር ግን #መልአኩ #ገብርኤልም፣ #ኤልሳቤጥም የተናገሩት አንድ አይነት ቃል <<ከሴቶች በላይ፣ ከፍጡራን ሁሉ በላይ>> ሳይሆን <<ከሴቶች #መካከል>>…
▶️ እስቲ እነዚህን ጥቅሶች ይመልከቷቸው።

〽️ ሐዋ 1፤ 9-11፦

<<ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።>>

⁉️ #ኢየሱስ ወደ #ሰማይ ሲያርግ ሁሉም #ደቀመዛሙርትና #ሴቶች #ማርያምም ጭምር #በደብረ ዘይት ተራራ #ዕርገቱን ሲመለከቱ ሁለቱ #መላእክት በአጠገባቸው #ቆመው < #ለማርያም ብቻ> ወይም < #በማርያም #በኩል> ሳይሆን የተናገሩት ለሁሉም #በእኩል አይን <<የገሊላ ሰዎች ሆይ...>> በማለት ነበር።

〽️ ሐዋ 1፤ 12-14፦

<<በዚያን ጊዜ ደብረ ዘይት ከሚባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ እርሱም ከኢየሩሳሌም የሰንበት መንገድ ያህል የራቀ ነው። በገቡም ጊዜ ወደሚኖሩበት ሰገነት ወጡ፥ ጴጥሮስና ዮሐንስም፥ ያዕቆብም፥ እንድርያስም፥ ፊልጶስም፥ ቶማስም፥ በርተሎሜዎስም፥ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም፥ ቀናተኛ የሚባለው ስምዖንም፥ የያዕቆብ ልጅ ይሁዳም። እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር።>>

⁉️ #ከክርስቶስ #እርገት ቡሀላ ወደ #ኢየሩሳሌም ሲመለሱ #ማርያም #ከሐዋሪያቶቹ ጋር ሌሎችም #በርካታ #ሴቶች ያለምንም #ልዩነት ለአንድነት #ለጸሎት #ይተጉ ነበር። ይህ ደግሞ #ማርያም #ከፍጡራን #የተለየች ወይም #ወጣ ያለች እንዳልነበረች አንብቦ #መረዳት አያቅትም።

〽️ ሐዋ 1፥15፦

<<በዚህም ወራት ጴጥሮስ መቶ ሀያ በሚያህል በሰዎች ማኅበር አብረው በነበሩ በወንድሞቹ መካከል ተነሥቶ አለ።>>

⁉️ የጸሎቱም #መሪ ሐዋሪያው #ጴጥሮስ ነበር እንጂ #ማርያም #ከጉባኤው ጋር #ምእመን ከመሆን ውጪ #የአምልኮው #መሪ እንኳን አልነበረችም። ይህ #ከፍጡራን #የተለየች ናት እንድንል አያደርገንም።

〽️ ሐዋ 1፥16፦

<<ወንድሞች ሆይ፥ ኢየሱስን ለያዙት መሪ ስለሆናቸው ስለ ይሁዳ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ይገባ ነበር፤>>

⁉️ ማርያም ባለችበት #ጉባኤ ተነስቶ <<ወንድሞች ሆይ>> በማለት #በቀጥታ #ንግግሩን ጀመረ እንጂ #በመካከላቸው ለነበረችው #ማርያም #ስግደት ወይም የተለየ #አክብሮት አላቀረበም። ይህም ከእነሱ #የተለየች እንዳልነበረች ያስረዳል።

〽️ ሐዋ 1፤ 21-22፦

<<ስለዚህ ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ፥ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ ከእኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፥ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል።>>

⁉️ አሁንም ሐዋሪያው #ጴጥሮስ #ማርያም ባለችበት በዚህ #ጉባዔ #በይሁዳ ምትክ ሌላ #ሐዋሪያ እንዲተካ #ሃሳብ ሲያቀርብ <<ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር #የትንሳኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል>> አለ እንጂ ስለ #ማርያም #ምስክር የሚሆን አለማለቱ በአሁኑ #ዘመን ለእኛ #ምስክርነታችን መሆን የሚገባው #ስለክርስቶስ እንጂ #ስለማርያም #መመስከር #የሐዋሪያት #ትምህርት እንዳልሆነ #የሚያስረዳ ነው።

〽️ ሐዋ 1፥25፦

<<ሲጸልዩም። የሁሉን ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ፥ ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ስፍራ ይሄድ ዘንድ በተዋት በዚህች አገልግሎትና ሐዋርያነት ስፍራን እንዲቀበል የመረጥኸውን ከእነዚህ ከሁለቱ አንዱን ሹመው አሉ።>>

⁉️ ይሄው ጉባዔ #ማርያም ባለችበት <<ሲጸልዩም የሁሉንም ልብ የምታውቅ አንተ ጌታ ሆይ>> ብለው #ቀጥታ ወደ #ጌታ ጸለዩ እንጂ እሷ #ከፍጡራን #በላይ ነች ብለው ወደ #ማርያም ወይም #በማርያም #ስም #አልጸለዩም። ይህም በግልጽ #ማርያም #ከሰው #የተለየች እንዳልሆነች ያሳያል።

〽️ ሐዋ 2፤ 1-4፦

<<በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው>>

⁉️ በዓለ #ሀምሳ የተባለውም #ቀን በደረሰ ጊዜ ሁሉም #በአንድ #ልብ ሆነው አብረው ሳሉ #መንፈስቅዱስ #በጉባዔው መካከል ከነበረችው #ከማርያም ወይም #በማርያም #በኩል ሳይሆን #ከሰማይ #መምጣቱ አንዳንዶች እንደሚሉት #ማርያም #መለኮታዊ መነሻ ወይም #ምንጭ ወይም #ሰጪ እንዳልሆነችም ያስረዳናል።

〽️ ሐዋ 2፤ 3-4፦

<<እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው። በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።>>

⁉️ #መንፈስቅዱስም ሲወርድ ሁሉም ላይ #እኩል ወረደ እንጂ #ለማርያም የተለየ #ጸጋ(መንፈስ) አለመሰጠቱ #በእግዚአብሄር ፊት ያው እንደማንኛውም #ክርስቲያን #እኩል እንደሆነች #እንጂ የተለየች ወይም #ከፍጡራን #የምትበልጥ እንደሆነች አያሳይም።

〽️ ሐዋ 2፤ 5-10፦

<<ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤ ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ። ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ። እነሆ፥ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን?...>>

⁉️ #በኢየሩሳሌም ይኖሩ የነበሩት #አይሁዶች በሁሉም ላይ #ከወረደው #ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ በገዛ #ቋንቋዎቻቸው ሲናገሩ እየሰሙ በሁሉም ተገረሙ እንጂ #ለማርያም የተለየ #አትኩሮት አልሰጡም። ይህም #ማርያም እንደነሱ #እኩል #ማንነትና #ጸጋ እንደነበራት ያሳያል።

〽️ ሐዋ 2፤ 9-12፦

<<የጳርቴና የሜድ የኢላሜጤም ሰዎች፥ በሁለት ወንዝም መካከል በይሁዳም በቀጰዶቅያም በጳንጦስም በእስያም፥ በፍርግያም በጵንፍልያም በግብፅም በቀሬናም በኩል ባሉት በሊቢያ ወረዳዎች የምንኖር፥ በሮሜም የምንቀመጥ፥ አይሁድም ወደ ይሁዲነትም የገባን፥ የቀርጤስና የዓረብ ሰዎች፥ የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን።...>>

⁉️ እነዚህ #የኢየሩሳሌምና #የአረብ ሰዎች <<የእግዚአብሄርን ታላቅ ስራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን>> አሉ እንጂ አንዳንዶች እንደሚሉት #የማርያምን #ታላቅ #ስራ ሲናገሩ #ሰማን ስላላሉ እንደ ሐዋሪያት #ምስክርነታችን <<የእግዚአብሔርን ታላቅ ስራ>> እንጂ #ስለማርያም #መስበክ #የሀዋሪያት #ፈለግ እንዳልነበረ ያስተምረናል።
▶️ ክርስቶስ <<በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ>> ብለን እንድንጸልይ እንጂ ያስተማረን << #እመቤታችን ሆይ>> ብለን እንድንጸልይ አላስተማረንም። የተሰጠንም #መንፈስ #አባ #አባ ብለን የምንጮህበት #መንፈስ #ብቻ ነው እንጂ #እማ #እማ ብለን የምንጮህበት አይደለም [ሮሜ 8፥15]። <<ስምህ ይቀደስ>> እንድንል እንጂ << #ሰላምታ #ይገባሻል>> እንድንል <<በደላችንን ይቅር በለን>> እንጂ << #ይቅርታን #ለምኚልን ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን ዘንድ>> እንድንል አላስተማረንም። የሁለቱም #ጸሎቶች #አድራሻና #ፍሬ ነገራቸው #የሰማይና #የምድር #ርቀት ያክል ልዩነት ያላቸውና #የሚጣረሱ ናቸው።

▶️ ከክርስቶስ #ትምህርት ጋር ሌሎችንም <<የጸሎት መጻህፍት>> የተባሉትን ብናስተያያቸው
እንደ <<አንቀጸ ብርሃን መጽሀፍ>> << #ስምሽ #የተመሰገነ ነው>> እንድንል ሳይሆን <<ስምህ ይቀደስ>> እንድንል፤ እንደ <<ተአምረ ማርያም መጽሀፍ>> << #ድንግል ሆይ #ፈጥነሽ እንድትመጪ>> [43፥26] እንድንል ሳይሆን <<መንግስት ትምጣ>> ብለን የክርስቶስን #መንግስትህ መምጣት #በናፍቆት እንድንጠባበቅ፤ <<ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን>> በማለት የእርሱ #ሰማያዊ #ፍቃድ ብቻ በምድራችን እንዲሆን እንጂ እንደ ተአምረ ማርያም ጸሀፊ << #ፈቃድሽ #ይሁንልን ይደረግልን>> እንድንል አላስተማረንም [100 ፤ 29-32]። <<የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን>> በማለት #የዕለት #ኑሮአችንንም እንዲያቀናልን እንድንጸልይ እንጂ። እንደ <<መልክዓ ማርያም መጽሀፍ>> << #መጻህፍትሽ #የማዳን #እንጀራንና የተፈተነ #መድሀኒት መጠጥን ስለሚሰጡ #ሰላምታ ይገባል[ለእራኃትኪ]>> እንድንል አላስተማረንም። <<ኃጢአታችንን ይቅር በለን>> እንድንል እንጂ እንደ <<መልክዓ ማርያም>> ደራሲ << #ኃጢአታችንን #ይቅር #በይን[ለመዛርዕኪ]>> እንድንል አላስተማረንም። <<ከክፉ አድነን>> በማለት #ከክፉ እንዲያድነን ወደ #እግዚአብሔር እንድንጸልይ እንጂ << #ከአዳኝ #አውሬ #አድኝኝ>> [የዘውትር ጸሎት ሰላምለኪ] እንድንል አላስተማረንም። <<ኃይል ክብርም ምስጋናም ለዘላለም ድረስ ላንተ ይሁን>> እንድንል እንጂ እንደ <<ተአምረ ማርያምና እንደ ቅዳሴ ማርያም>> <<ድንግል ሆይ #ክብርና #ምስጋና #ለዘላለም ይገባሻል>> እንድንል አላስተማረንም። ስለሆነም ይህን #ከክርስቶስ #ትምህርት ጋር የሚጣረስ ትልቅ #ኑፋቄ ወደ #ቤተክርስቲያን ማስገባትና ማስተማር ታላቅ #በደልና #ኃጢአት ነው።

▶️ አንዳንድ #ሰዎች ደግሞ ይህን #ኑፋቄ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ለማስመሰል #ከሉቃስ ወንጌል 1፤ 28- ጀምሮ ያለውን ክፍል ይጠቅሳሉ።

በክፍሉ እንደሚነበበው ግን #መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል #ከእግዚአብሄር ዘንድ ተልኮ ወደ #ድንግል #ማርያም በመጣ ጊዜ በሚያስደንቅ #ሰላምታ ከተገናኘ ቡኃላ የተላከበትን ጉዳይ <<እግዚአብሔር #ከአንቺ ጋር ነው>> በማለት ስለሚወለደው ቅዱስ #የእግዚአብሄር #ልጅና #ስልጣን ላይ አተኩሮና #ሰፊ ጊዜ ወስዶ ሲያበስራት ልክ እንደ ማንኛውም ሰው ወደ #አንድ #ቤት ወይም #ከጓደኛው ጋር ሲገናኝ #አይነቱ ይለያል እንጂ #ሰላምታ መለዋወጥ በየትኛውም #ሀገር ያለና የተለመደ #ባህላዊ #ስርአት ስለሆነና በተለይም #በመንፈሳዊ ሰዎች ዘንድ ሲገናኙ #ሰላምታ መለዋወጥ #ልማድ ከመሆኑም ጭምር እንዲሁም #መጽሀፍ ቅዱሳዊ በመሆኑ [ማቴ 10፤ 12-13]። መለአኩ #ቅዱስ #ገብርኤልም ያደረገው ይኸንን ነው #ጸሎት እያቀረበ አለመሆኑን ማንም #ሰው አንብቦ #መረዳት የሚችለው ነገር ነው። #ማርያምም ለቀረበላት ሰላምታ <<ይህ #እንዴት ያለ #ሰላምታ ነው>> ብላ አሰበች እንጂ እንደ #ጸሎት #ተቀባይ ወይ እንደ #ጸሎት #ሰሚ ሆና አልቀረበችም [ሉቃ 1፥29]። ነገር ግን አንዳንዶች ይህን ክፍል በመጥቀስ #ማርያምን <<በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ #ሰላም #እልሻለው>> እንዲባል #አስተምረዋል ጽፈው አልፈዋልም ዛሬም #የሚያስተምሩ አልጠፉም።
▶️ የማርያም #መጻሕፍት አብዛኞቹ እንደነ <<ውዳሴ ማርያም>>፣ <<ቅዳሴ ማርያም>> የመሳሰሉት #የእግዚአብሔርን ቃል ወስደው ወደ #ማርያም የማጠጋጋት #ባህሪ አላቸው። በሌላ በኩል ደግሞ #የተጋነኑና #አሳፋሪ #ሐሰት ይገኝባቸዋል። #የእግዚአብሔር ቃል #እውነትን በእጅጉ ይቃረናሉ ለምሳሌ <<መጽሐፈ አርጋኖን[1]>> የተባለው ፦

〽️ <<አዳም ከልጆቹ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12 ክፍል 8፤ ቁ.6]
〽️ <<ኖህ ከልጆቹ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12 ክፍል 8፤ ቁ.9]
〽️ <<አብርሃም ከሳራ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.10]
〽️ <<ይስሐቅ ከርብቃ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.11]
〽️ <<ዕብራዊው ያዕቆብም ከልጁ ከይሁዳ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.14]
〽️ <<ሙሴ ከእስራኤል ልጆች ሁሉ ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.20]
〽️ <<ዳዊት ከመዘምራን ጋር ያመሰግንሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.23]
〽️ <<ማህበረ መላዕክት ያመሰግኑሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.26]
〽️ <<ማህበረ ነብያት ሁሉም ያመሰግኑሻል>> [ምዕ 12፤ ክፍል 8፤ ቁ.27]

▶️ እነዚህ የተጠቀሱ #የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ሲሆኑ ክፍሎቹን ወደ #መጽሐፍ ቅዱስ ሄደን #በጥሞና ብናነባቸው የሚነግሩን፦ #አዳም #ከልጆቹ ጋር #እግዚአብሔርን እንጂ #ማርያምን አላመሰገነም። ጭራሽ #አይተዋወቁም። በመካከላቸው ያለው #የዘመን ልዩነት #የሰማይና #የምድር ርቀት ያክል ነውና። [ዘፍ 4፥3፣ ዘፍ 5፤ 1-5]። #ኖህ ከልጆቹ ጋር [ዘፍ 6፥9፣ ዘፍ 8፤ 20-22፣ ዕብ 11፥7] #አብርሃም ከሣራ ጋር [ዘፍ 28፥8፣ ዘፍ 21፥1፣ ዕብ 11፥8፣ 19] #ይስሐቅ #ከርብቃ ጋር [ዘፍ 27፥27]፣ #ያዕቆብም [ዘፍ 28፤ 18-22፣ ዕብ 11፥20]፣ #ሙሴ #ከእስራኤላውያን ጋር [ዘጸ 15፤ 1-26፣ ዕብ 11፤ 23-28]፣ #ዳዊትም [2ሳሙ 6፤ 12-33፣ መዝ 8፤ 1-9] #ማህበረ #መላእክትም [ኢሳ 6፥3፣ ራዕ 4፤ 7-11]። #የሐዋርያት ማህበርም [ሐዋ 2፤ 46-47፣ ሐዋ 16፥25]፣ ሁሉም በግልጽ #እግዚአብሔርን ብቻ እንዳከበሩ እንጂ #ማርያምን ያመሰግኑበትም ሆነ #ስሟን እንኳን የጠሩበት አንድም #ቦታ የለም።

▶️ ስለሆነም <<ማርያምን ያመሰግናሉ>> የሚለው #ኢ-መጽሐፍቅዱሳዊና #የነብያትን#የመላእክትን፣ እንዲሁም #የሐዋርያትን ስም ማጥፋትና #ለእግዚአብሔር ያቀረቡትን የተባረከ #ምስጋናቸውን ወደራስ #ሃሳብና #መሻት ለመጠምዘዝ የተደረገ ከንቱ #የባእድ #አምልኮ #ሙከራ ነው።

ሌላው #ውሸት የታጨቀበት #መጽሐፍ ደግሞ <<መጽሐፈ ሰዓታት[2]>> የተባለው #መጽሐፍ ነው። ለምሳሌ ያክል

〽️ <<ለመጸብሐዊ ማቴዎስ እንተ ረሰይኪዩ ወንጌላዊ - ለቀራጩ ማቴዎስ ወንጌላዊ ያደረግሽው አንቺ ነሽ>> ይላል [መጽሐፈ ሰዓታት ርኅርኅተ ህሊና ገጽ 132 - 133]። ነገር ግን #ማቴዎስ ወደ #ወንጌላዊነት እንዴት እንደመጣ #ራሱ #ስለራሱ ሲናገር <<ኢየሱስም ከዚያ አልፎ በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው አየና። ተከተለኝ አለው። ተነሥቶም ተከተለው።>> [ማቴ 9፥9] ብሏል። ይህንን #መጽሐፍ ቅዱሳዊ #እውነት ክዶ #ማርያም #ማቴዎስን #ወንጌላዊ አደረገችው ማለት ምን ይሉታል?

▶️ ማህሌተ ጽጌ የተባለው #መጽሐፍ ደግሞ <<ቅዱስ ጴጥሮስ በ30 እስታቴር (በ30 ብር) በርተሎሜዎስን ለግብርና ስራ ሸጠው>> ይላል። በመቀጠልም <<የጴጥሮስ ጥላው የጳውሎስም ልብሱ ማርያም አንቺ ነሽ>> ይላል። አንባቢ ሆይ አረ #እናስተውል!!። ሐዋርያው #ጴጥሮስ ሐዋርያው #በርተሎሚዎስን እንደሸጠ ከየት የተገኘ #ወሬ ነው?። #ከታሪክ አንጻር እንኳን ብንመለከተው #ጴጥሮስም #በርተሎሚዎስም #ለወንጌል አገልግሎት ከመጠራታቸው በፊት #በሮማ ግዛት ስር የነበሩ ተራ #አይሁዳውያን ነበሩ እንጂ #ሰውን የሚሸጡ #ገዢዎች እንኳ አልነበሩም። ታድያ ሐዋርያው #ጴጥሮስ የወንጌል ጓደኛውን #በርተሎሜዎስን #ለግብርና ስራ #በ30 ብር ሸጠ ማለትና #የጴጥሮስ ጥላው #የጳውሎስም የልብሱ ዘርፍ #በሽተኞችን ሲፈውስ #ፈዋሹ #እግዚአብሔር ብቻ ሆኖ ተጽፎ እያለ <<ጥላና ልብሱ ማርያም ነበረች>> ማለት አያሳተዛዝብም? [ሐዋ 5፤ 15-16፣ 19፤ 11-12]። አረ ያስተዛዝበናል!

▶️ ይህ በብዙ የሳተ #መጽሐፍ #በግእዝና #በዜማ ለህዝቡ ስለሚቀርብለት አብዛኛው #ቋንቋውን ስለማያውቅ የሚባለውን #ሳይሰማና #ሳያስተውል #አሜን ብሎ ይሄዳል። ምናልባት ጉዳዩን በጥሞና #መረዳት ቢችልና ለማረም ቢሞክር ደግሞ #ተሐድሶ#መናፍቅ ወ.ዘ.ተ ተብሎ #የውግዘት ናዳው ይዘንብበታልና አብዛኛው #ዝም ማለቱን የመረጠ ይመስላል።

<<ሰውም ሁሉ ባልንጀራውን ያታልላል በእውነትም አይናገርም፤ ሐሰትን መናገርንም ምላሳቸው ተምሮአል፥ ክፉንም ለማድረግ ይደክማሉ። ማደሪያህ በሽንገላ መካከል ነው፥ ከሽንገላም የተነሣ እኔን ያውቁኝ ዘንድ እንቢ ብለዋል፥ ይላል እግዚአብሔር።>> [ኤር 9፤ 5-6]።

✔️ ከተጻፈው አትለፍ /1ኛ ቆሮ 4-6/

🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆

"ማጣቀሻዎች - References"
_________
[1] 📚፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ አርጋኖን የእመቤታችን ምስጋና፤ ተስፋ ገብረስላሴ ማተሚያ ቤት፡ አ.አ፥ 1989 ዓ.ም።

[2] ሰፊ ማብራሪያ
📚፤ GBV <መጽሀፈ ሰአታት በመቅደሱ ሚዛን> 2ተኛ ዕትም ጥቅምት፡ 1995 ዓ.ም፤ BGNLJ፤ አ.አ፥ ኢትዮጵያ።
ይመልከቷል።

@gedlatnadersanat
(8.6.6▶️) ይቀጥላል...
@gedlatnadersanat