Audio
ውይይት
#በእንተ_ገብርሔር
ክፍል ሦስት
በወንድሞቻችን
#ዮሴፍ_ዘለቀ
#ኢዮብ_ክንፈ
#ተርቢኖስ_ሰብስቤ
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#በእንተ_ገብርሔር
ክፍል ሦስት
በወንድሞቻችን
#ዮሴፍ_ዘለቀ
#ኢዮብ_ክንፈ
#ተርቢኖስ_ሰብስቤ
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
❤ #በዓለ_ወልድ❤
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።የሚኰንንስ ማንነው?የሞተው ይልቁንም በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፤ደግሞም ስለኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።" (ሮሜ 8:34)
ይህ የብርሃነ ዓለም የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የቅድስት ቤተክርስትያናችን የሃይማኖት ጸሎት ነው።
በቅድስት ቤተክርስቲያን የምናምነውን እንጸልያለን፤ የምንጸልየውን እናምናለን።በሌላ አነጋገር ሃይማኖታችንን እንጸልየዋለን ፤ ጸሎታችንም ሃይማኖታችን ነው።ሃይማኖት በእግዚአብሔር ማመን፤በእርሱ መታመን ፤ እርሱንም ብቻ ተስፋ ማድረግ ነው።ሃይማኖታችን ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው።ሃይማኖትን የሰጠንም እግዚአብሔር ነው።"ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሃይማኖት" እንዲል (ይሁዳ 1:3)።በመሆኑም ከእግዚአብሔር የተሰጠንን ሃይማኖት ( በእርሱ ማመንን ) ለሰጠን ለእርሱ በጸሎት መልክ እናቀርበዋለን።ይህንንም የምናደርገው እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን ነገር ፍለጋ ነው።"ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም"ና (ዕብ 11:6)።
በነቢያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ የተመሠረተች የማዕዘኗ ራስ ድንጋይም ኢየሱስ ክርስቶስ የሆነላት (ኤፌ 2:20) ቅድስት ቤተክርስቲያን የሐዋርያው ሃይማኖት ሃይማኖቷ ነውና ትጸልየዋለች።የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን እንዴት እንደምትጸልየው ከመመልከታችን በፊት የቃሉን መልእክት በአጭሩ እንመልከት።
"የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው" ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት "ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ" (ከጻድቅ ጋር ጻድቅ ትሆናለህ) ማለትም ለጻድቅ የጽድቁን ዋጋ ትሰጠዋለህ(መዝ 17:25) በማለት እንደተናገረው ለጻድቃን ጽድቃቸውን መስክሮ ዋጋቸው መንግሥተሰማያትን ሰጥቶ የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው።
"የሚኰንንስ ማንነው?" አልመለስ የሚሉትን በሥጋ የሚቀስፋቸው በነፍስ የሚፈርድባቸው ማን ነው? አንድም በርቱዕ ፍርዱ ሥጋንም ነፍስንም በአንድነት በገሃነም የሚቀጣ ማንነው?(ማቴ 10:28)
"የሞተው" በዕፀ መስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ከክብርት ነፍሱ በመልካም ፈቃዱ የለየው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በሞቱ ጊዜም ፈርዷል።በቀኙ የተሰቀለውን ሲያጸድቀው (የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነውና) በግራው የተሰቀለውን ኰንኖታል።ሞቱም መፋረጃ ነው፤በሞቱ ያመኑ ሲድኑ ያላመኑት ግን ይኰነናሉ።
"ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው" በኩረ ትንሣኤአችን ሆኖ በባሕርይ ሥልጣኑ ከሞት የተነሣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በትንሣኤውም ጊዜ ፈርዷል።"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ።የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ጠላቶቹን በኋላቸው መታቸው የዘለዓለምን ኀሣር ሰጣቸው።"(መዝ 77:65-66) ተብሎ እንደተነገረ የትንሣኤው ተቃዋሚ የሆኑትን አይሁድን፣መናፍቃንንና አጋንንትን ሲፈርድባቸው በአንጻሩ ትንሣኤውን በፍጹም ልባቸው ያመኑትን ሐዋርያትን እስከ ምድር ዳር ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች አድርጓቸዋል(ሐዋ 1:8 ና 21-22)የጌታ ትንሣኤውም መፋረጃ ነው።በትንሣኤው ያመኑት ሲድኑ ያላመኑት ግን ይፈረድባቸዋልና።
"በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው" በእግዚአብሔርነቱ ሥልጣን የሚኖር አንድም በአምላክነቱ ከአባቱ እኩል የሆነው ንጉሣችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።እንግዲህ እግዚአብሔር ከሆነ ሥራው ምንድንነው መሥራት መቅጻት፣ማምሸት ማንጋት፣መግደል ማዳን፣ማጽደቅ መኰነን፤ሥነፍጥረትን ሁሉ ማስተዳደር ነው።ይህ ሁሉ የፍርድ ሥራ ይባላል።ሞቱም ትንሣኤውም መፋራጃ የሆነው ከእርሱ ፈራጅነት (እግዚአብሔርነት ) የተነሣ ነው።
"ስለኛ የሚማልደው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" አንድ ጊዜ ፈጽሞ ባቀረባት የዘለዓለማዊ ክህነት አገልግሎት (ለዘለዓለም የሚሆን መሥዋዕት አቅራቢነት) ያዳነን ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።"የሚማልደው" የሚለው ቃል በትንቢት አንቀጽ (future tense) ቢጻፍም የሚገልጸው ግን የተፈጸመን ድርጊት ነው።እንዲህ ያሉ አገላለጾች በቅዱሳት መፃሕፍት ይገኛሉ።ለምሳሌ"ሕፃን ተወልዶልናልና" ተብሎ የተነገረው ወደፊት ስለሚወለደው አምላካችን ነው።"እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዓት አንተ ለዘለዓለም ካህን ነህ"(መዝ 109:4) ተብሎ የተነገረለት አምላካችን የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ይፈርድ እንደነበር ለዘለዓለሙ የሚፈርድ ነው።ይህች የክህነት አገልግሎቱም መፋረጃ ናት።በዚህ የዘለዓለም ክህነት አገልግሎቱ የሠዋውን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የተቀበለ ሲድን ያልተቀበለ ግን ይፈረድበታልና። ይህ ሁሉ በጥቅሉ የሚያጸድቅም የሚኰንንም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ማለት ነው።ሞቱም፣ትንሣኤውም፣ዳግም ምጽአቱም በቅድስት ቤተክርስቲያን በዓላተ ወልድ (የወልድ በዓላት) ናቸው።
የካቲት 29/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
ይጠጣ ነበር።(1ኛ ነገ 17:2-6) በጥቂት ብቻ በእግዚአብሔር ተአምር የኖሩ ቅዱሳን ብዙ ናቸው።በተለይም ርእሰ ባሕታውያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ናቸው።562 ዓመት ሙሉ የእናታቸውን ጡት ጨምሮ ያለ ምግብ ፣ ያለ ልብስና ያለ መጠለያ በጾምና በጸሎት ያውም ከብዙ ሺ ስግደቶችና ተጋድሎዎች ጋር ተጸምዶ መኖር ያልተደነቀ ምን ይደነቃል!?ይኸውም የሆነው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል (በተአምር) ነው እንጂ በሌላ አይደለም።እግዚአብሔር "ይሁን" ያለው ይሆናል፤"ይሁን" ያላለውም አይሆንምና።በተፈጥሮ ለሰው ምግብ እንዲያስፈልገው ያደረገ አምላክ እንዳያስፈልገውም ማድረግ ይችላል።አሁንም ቢሆን በጥቂት ብቻ በበረከቱ የሚያኖራቸው ደጋግ ክርስቲያኖች ሞልተዋል።
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
"ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል" አካላዊ ቃል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ስለዚህ በእርሱ በማመን በሃይማኖት በር ገብተን፤በቀጠነችው መንገድ በፈቃደ ነፍስ ተጉዘን፤ሕይወት የሆነው እርሱ ጋር ደርሰን በሕይወት እንኖራለን።ይህንን ሐሳብ ራሱ አምላካችን እንዲህ ሲል ገልጦታል።"በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።" (ማቴ 7:13) ስለዚህ ሰው ጠባብ በር በተባለው በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክነትና የዘለዓለም ሕይወትነት (1ኛ ዮሐ 5:20) አምኖ ፤ በቀጠነው መንገድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ተጉዞ ፤ የአካላዊ ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ፤ራሱ ሕይወት የሆነው እግዚአብሔር ጋር ይደርሳል።መነሻውም መገስገሻውም መዳረሻውም እውነተኛ አምላኩ ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል ማለት ነው።እግዚአብሔር በቸርነቱ ጾሙን ስስትን ድል የምንነሣበት ያድርግልን!!!
መጋቢት 2/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዕርገተ ክርስቶስ እንደ ሃይማኖት"
#በጸሎተ ሃይማኖታችን ከምንመሰክራቸው ምስክርነቶች አንዱ "በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ" የሚል ነው።በዚህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በኋላ እንዳረገ ማመናችንን እንገልጣለን።ይህንን ሃይማኖታችንን ያገኘነውም "የእግዚአብሔር መንፈስ ካለባቸው" ቅዱሳት መጻሕፍት ነው።(2ኛ ጢሞ 3:16)
ቅዱስ ዳዊት "በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" (መዝ 67:33) ቅዱስ ሉቃስ ደግሞ "ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ" (ሉቃ 24:51) ብለውናል።እነዚህም የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነቶች ናቸው።
"ዕርገተ ክርስቶስ በነገረ ማርያም"
#የእመቤታችን ወዳጅ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ" ሲል ያመሰግናታል።ይኸውም ለቃል ርደት(መውረድ (ሰው መሆን) ) ለሥጋ ዕርገት ( ከፍ ማለት (አምላክ መሆን) )ምክንያት ድንግል ማርያም ናት ማለት ነው።ቃል ሥጋ ሲሆን ሥጋም ቃልን በመሆን ከፍ ያለው (ያረገው) በማኅፀነ ድንግል ማርያም ነው።ኋላም ከተነሣ በዐርባኛው ቀን ያረገው ከእመቤታችን ሰው በሆነበት ሥጋ ነው።በዕርገቱ ጊዜ ከእናቱ የነሣው (የተዋሐደው) ሥጋ አልተለየውም።"በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ..." በሚለው ኃይለቃል ውስጥ ያለው "ምሥራቅ" የሚለው ቃልም "ሥጋ ማርያም"ን ያሳያል።ጌታ ፀሐየ ጽድቅ ሆኖ ከእርሷ የወጣባት ምሥራቅ ድንግል ማርያም ናትና።ስለዚህ ኃይለ ቃሉ "በድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ተብሎ ይተረጎማል።
"ዕርገተ ክርስቶስ በአምልኮአችን"
#ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትገለጥበት ትልቁ አምልኮዋ ቅዳሴ ነው።የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ "አሜን" ( አሜን ለሃይማኖት ሲሆን ትክክል/እውነት ማለት ነው) እያለች ከምትናገራቸው ምስክርነቶቿ አንዱ "ነአምን ዕርገተከ ወዳግመ ምጽአተከ" (ዕርገትህን እናምናለን ሁለተኛ መምጣትህንም) የሚል ነው።እንዲሁም ካህኑ "አልዕሉ አልባቢክሙ" (ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ) በማለት ከፍ ከፍ ያለውን አምላካችንን ሲያሳስበን ዲያቆኑ ደግሞ "ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ" ብሎ የጌታን በምሥራቅ ማረግ ያስታውሰናል።ልቡናን ከፍ ከፍ ማድረግም በዓይነ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር ጌታን ሲያርግ መመልከት ፤ በዕዝነ ልቡና የቅዱሳን መላእክቱን ዝማሬ ማድመጥ፤ በአንፈ ልቡና መዓዛ ዕርገቱን ማሽተት ፤ በእግረ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር በደብረ ዘይት መቆም፤በአብራከ ልቡና ለጌታችን መስገድና በዚህ ሁሉ መደሰት ነው።"እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" እንዲል (ሉቃ 24:52)
"ዕርገተ ክርስቶስ በክርስቲያናዊ ሕይወት"
#ጌታችን ወደ ላይ ከፍ ከፍ እንዳለ ክርስትናም ከፍ ከፍ የማለት ሕይወት ነው።ተወዳጅ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ "በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል" (1ኛ ዮሐ 2:6) እንዳለ ጌታችን ከፍ ከፍ እንዳለ እኛም በቅድስና ከፍ ከፍ ልንል ይገባናል።ይህ የቅድስና ሕይወትም ከሥጋ ንጽሕና ወደ ነፍስ ንጽሕና ከነፍስ ንጽሕና ወደ ልቡና ንጽሕና የሚደረግ ጉዞ ነው።ከሁሉ አስቀድመን ግን ከስድብ ወደ ምስጋና፣ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ከቂም ወደ ይቅርታ፣ከዓለም ወደ ቤተክርስቲያን፣ከፍልስፍና ወደ ሃይማኖት፣ከገዛ አጉል እሳቤአችን ወደ እግዚአብሔር ሐሳብ ከፍ ከፍ ልንል ያስፈልገናል!!!
"ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው ፤ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን።" (2ኛ ተሰ 4:17)
መድኃኔዓለም እንዲህ ያለውን የክብር መነጠቅ በቸርነቱ ያድለን !!!
ሰኔ 07/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#በጸሎተ ሃይማኖታችን ከምንመሰክራቸው ምስክርነቶች አንዱ "በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ" የሚል ነው።በዚህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በኋላ እንዳረገ ማመናችንን እንገልጣለን።ይህንን ሃይማኖታችንን ያገኘነውም "የእግዚአብሔር መንፈስ ካለባቸው" ቅዱሳት መጻሕፍት ነው።(2ኛ ጢሞ 3:16)
ቅዱስ ዳዊት "በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" (መዝ 67:33) ቅዱስ ሉቃስ ደግሞ "ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ" (ሉቃ 24:51) ብለውናል።እነዚህም የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነቶች ናቸው።
"ዕርገተ ክርስቶስ በነገረ ማርያም"
#የእመቤታችን ወዳጅ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ" ሲል ያመሰግናታል።ይኸውም ለቃል ርደት(መውረድ (ሰው መሆን) ) ለሥጋ ዕርገት ( ከፍ ማለት (አምላክ መሆን) )ምክንያት ድንግል ማርያም ናት ማለት ነው።ቃል ሥጋ ሲሆን ሥጋም ቃልን በመሆን ከፍ ያለው (ያረገው) በማኅፀነ ድንግል ማርያም ነው።ኋላም ከተነሣ በዐርባኛው ቀን ያረገው ከእመቤታችን ሰው በሆነበት ሥጋ ነው።በዕርገቱ ጊዜ ከእናቱ የነሣው (የተዋሐደው) ሥጋ አልተለየውም።"በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ..." በሚለው ኃይለቃል ውስጥ ያለው "ምሥራቅ" የሚለው ቃልም "ሥጋ ማርያም"ን ያሳያል።ጌታ ፀሐየ ጽድቅ ሆኖ ከእርሷ የወጣባት ምሥራቅ ድንግል ማርያም ናትና።ስለዚህ ኃይለ ቃሉ "በድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ተብሎ ይተረጎማል።
"ዕርገተ ክርስቶስ በአምልኮአችን"
#ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትገለጥበት ትልቁ አምልኮዋ ቅዳሴ ነው።የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ "አሜን" ( አሜን ለሃይማኖት ሲሆን ትክክል/እውነት ማለት ነው) እያለች ከምትናገራቸው ምስክርነቶቿ አንዱ "ነአምን ዕርገተከ ወዳግመ ምጽአተከ" (ዕርገትህን እናምናለን ሁለተኛ መምጣትህንም) የሚል ነው።እንዲሁም ካህኑ "አልዕሉ አልባቢክሙ" (ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ) በማለት ከፍ ከፍ ያለውን አምላካችንን ሲያሳስበን ዲያቆኑ ደግሞ "ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ" ብሎ የጌታን በምሥራቅ ማረግ ያስታውሰናል።ልቡናን ከፍ ከፍ ማድረግም በዓይነ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር ጌታን ሲያርግ መመልከት ፤ በዕዝነ ልቡና የቅዱሳን መላእክቱን ዝማሬ ማድመጥ፤ በአንፈ ልቡና መዓዛ ዕርገቱን ማሽተት ፤ በእግረ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር በደብረ ዘይት መቆም፤በአብራከ ልቡና ለጌታችን መስገድና በዚህ ሁሉ መደሰት ነው።"እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" እንዲል (ሉቃ 24:52)
"ዕርገተ ክርስቶስ በክርስቲያናዊ ሕይወት"
#ጌታችን ወደ ላይ ከፍ ከፍ እንዳለ ክርስትናም ከፍ ከፍ የማለት ሕይወት ነው።ተወዳጅ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ "በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል" (1ኛ ዮሐ 2:6) እንዳለ ጌታችን ከፍ ከፍ እንዳለ እኛም በቅድስና ከፍ ከፍ ልንል ይገባናል።ይህ የቅድስና ሕይወትም ከሥጋ ንጽሕና ወደ ነፍስ ንጽሕና ከነፍስ ንጽሕና ወደ ልቡና ንጽሕና የሚደረግ ጉዞ ነው።ከሁሉ አስቀድመን ግን ከስድብ ወደ ምስጋና፣ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ከቂም ወደ ይቅርታ፣ከዓለም ወደ ቤተክርስቲያን፣ከፍልስፍና ወደ ሃይማኖት፣ከገዛ አጉል እሳቤአችን ወደ እግዚአብሔር ሐሳብ ከፍ ከፍ ልንል ያስፈልገናል!!!
"ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው ፤ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን።" (2ኛ ተሰ 4:17)
መድኃኔዓለም እንዲህ ያለውን የክብር መነጠቅ በቸርነቱ ያድለን !!!
ሰኔ 07/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from Eyob kinfe
❤ "ሕይወትን በሚሰጥ አዳኝ በሆነ ከአብ በሠረጸ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን" (ጸሎተ ሃይማኖት)❤
#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።
#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።
#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።
#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።
#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።
#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።
#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።
#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።
#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።
#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።
#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።
#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።
#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።
#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።
#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
"ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሣራ ተመልከቱ።" (ኢሳ 51:2)
ነቢዩ ይህንን ቃል ቅዱስ አብርሃምንና ቅድስት ሣራን ምሰሏቸው ለማለት ተናግሮታል።
#አብርሃም አበ መናንያን (የመናንያን አባት) ነው።ሁሉን ትቶ እግዚአብሔርን ተከትሎአልና።(ዘፍ 12:1)
#አብርሃም የሙሽሮችም አባት ነው።ሚስቱ ምን መካን ብትሆን አልተዋትምና።
#አብርሃም ለሰብዓ ዓለም (በዓለም ለሚኖሩ ክርስቲያኖች) አባት ነው።በሕገ ልቡና ሁኖ ወንጌልን ፈጽሟልና።አረ ግሩም ነው !!! የእግዚአብሔር እንግዳ ቤቴ ሳይመጣ ግብር አላገባም፤እህል አልቀምስም ማለት እንዴት ያለ ብፅዕና ነው!? ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅረ ቢጽ እንዴት ቢጸኑለት ነው!?ደጉ አባታችን የእግዚአብሔር ሰው አብርሃም ወንጌልን ሲፈጽማት ተመልከቱልኝማ!!!
#"በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና"(ማቴ 5:3) ትሑቱ አብርሃም ባለጠጋ ሆኖ ሳለ ለእኔ የሚስማማ ደህነትነው፤ባለጠግነትማ የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው በማለት መንፈሱን ዝቅ አድርጎ ራሱን እንዳሳላፊ ቆጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ለሌሎች ያካፍል ነበር።በዚህም መንግሥተ ሰማያት (የሰማያት መንግሥት) የሆኑ ሥላሴን አስተናግዷል።መንግሥተ ሰማያት የሚባል ጌታም ከእርሱ ዘር ተወልዷል።"የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።"ማቴ 1:1እንዲል
#“የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።”
(ማቴ 5:4) ርኅሩኁ አብርሃም ለሦስት ቀናት ያህል ሰው ቤቱ ስላልመጣ እጅጉን አዝኗል።ሥላሴን በማግኘት ተጽናንቷል።
#"ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።"(ማቴ 5:6) መፍቀሬ ሰብእ ደጉ አብርሃም ስለ ሰው ፍቅር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ተርቧል።ጽድቅ የሚባል እግዚአብሔርን በድንኳኑ ተቀብሎም ጠግቧል (ነፍሱ ተደስታለች) ።
#"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።"(ማቴ 5:10) የሃይማኖት ሰው አብርሃም እግዚአብሔር "ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"(ዘፍ 12:1) ሲለው በፍጹም እምነት ወጥቷል።መንግሥቱንም ወርሷል።
"አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፤አየም ደስም አለው።" ዮሐ8:56 ማለት እንግዲህ ይህ ነው።በጨለማው ዘመን ሆኖ ብርሃንን ማየት ወንጌልን መኖር!!!ቅድስት ሥላሴን በቤቱ ተቀብሎ"የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተእመለሳለሁ፤ሣራምልጅንታገኛለች።"ዘፍ18፤14 ባለው ቃል መሠረት ለጊዜው ይስሐቅን እንደሚወልድ ለፍጻሜው ክርስቶስ ከእርሱ እንደሚወለድ ኪዳንን ተቀብሏል።
#በሕገ ልቡና ሕገ ኦሪት በሕገ ኦሪት ሕገ ወንጌል በተሰጠን በእኛ ቅዱስ አብርሃም ይፈርዳል፤ከአብርሃም የሚከብር ጌታ በሥጋ አብርሃም ተወልዶ በጥምቀት ልጅነትን፣በልጅነት መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶን የአብርሃምን ሥራ አልሠራንምና።
የአብርሃሙ ሥላሴ በሁላችን ቤት ይደሩ!!!
ሐምሌ ሥላሴ/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
ነቢዩ ይህንን ቃል ቅዱስ አብርሃምንና ቅድስት ሣራን ምሰሏቸው ለማለት ተናግሮታል።
#አብርሃም አበ መናንያን (የመናንያን አባት) ነው።ሁሉን ትቶ እግዚአብሔርን ተከትሎአልና።(ዘፍ 12:1)
#አብርሃም የሙሽሮችም አባት ነው።ሚስቱ ምን መካን ብትሆን አልተዋትምና።
#አብርሃም ለሰብዓ ዓለም (በዓለም ለሚኖሩ ክርስቲያኖች) አባት ነው።በሕገ ልቡና ሁኖ ወንጌልን ፈጽሟልና።አረ ግሩም ነው !!! የእግዚአብሔር እንግዳ ቤቴ ሳይመጣ ግብር አላገባም፤እህል አልቀምስም ማለት እንዴት ያለ ብፅዕና ነው!? ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅረ ቢጽ እንዴት ቢጸኑለት ነው!?ደጉ አባታችን የእግዚአብሔር ሰው አብርሃም ወንጌልን ሲፈጽማት ተመልከቱልኝማ!!!
#"በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና"(ማቴ 5:3) ትሑቱ አብርሃም ባለጠጋ ሆኖ ሳለ ለእኔ የሚስማማ ደህነትነው፤ባለጠግነትማ የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው በማለት መንፈሱን ዝቅ አድርጎ ራሱን እንዳሳላፊ ቆጥሮ እግዚአብሔር የሰጠውን ለሌሎች ያካፍል ነበር።በዚህም መንግሥተ ሰማያት (የሰማያት መንግሥት) የሆኑ ሥላሴን አስተናግዷል።መንግሥተ ሰማያት የሚባል ጌታም ከእርሱ ዘር ተወልዷል።"የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ።"ማቴ 1:1እንዲል
#“የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።”
(ማቴ 5:4) ርኅሩኁ አብርሃም ለሦስት ቀናት ያህል ሰው ቤቱ ስላልመጣ እጅጉን አዝኗል።ሥላሴን በማግኘት ተጽናንቷል።
#"ስለ ጽድቅ የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።"(ማቴ 5:6) መፍቀሬ ሰብእ ደጉ አብርሃም ስለ ሰው ፍቅር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ተርቧል።ጽድቅ የሚባል እግዚአብሔርን በድንኳኑ ተቀብሎም ጠግቧል (ነፍሱ ተደስታለች) ።
#"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።"(ማቴ 5:10) የሃይማኖት ሰው አብርሃም እግዚአብሔር "ከአገርህ ከዘመዶችህም ከአባትህም ቤት ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ።"(ዘፍ 12:1) ሲለው በፍጹም እምነት ወጥቷል።መንግሥቱንም ወርሷል።
"አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፤አየም ደስም አለው።" ዮሐ8:56 ማለት እንግዲህ ይህ ነው።በጨለማው ዘመን ሆኖ ብርሃንን ማየት ወንጌልን መኖር!!!ቅድስት ሥላሴን በቤቱ ተቀብሎ"የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተእመለሳለሁ፤ሣራምልጅንታገኛለች።"ዘፍ18፤14 ባለው ቃል መሠረት ለጊዜው ይስሐቅን እንደሚወልድ ለፍጻሜው ክርስቶስ ከእርሱ እንደሚወለድ ኪዳንን ተቀብሏል።
#በሕገ ልቡና ሕገ ኦሪት በሕገ ኦሪት ሕገ ወንጌል በተሰጠን በእኛ ቅዱስ አብርሃም ይፈርዳል፤ከአብርሃም የሚከብር ጌታ በሥጋ አብርሃም ተወልዶ በጥምቀት ልጅነትን፣በልጅነት መንግሥተ ሰማያትን ሰጥቶን የአብርሃምን ሥራ አልሠራንምና።
የአብርሃሙ ሥላሴ በሁላችን ቤት ይደሩ!!!
ሐምሌ ሥላሴ/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
እመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እንደ ልጇ ተነሥታ ዐርጋለች።"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት"(መዝ 131:8) በማለት ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት የጌታችንና የእናቱን የእመቤታችንን ትንሣኤ አስተባብሮ ተናግሯል።"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ" ብሎ የጌታን "አንተና የመቅደስህ ታቦት" በማለት ጌታችን ብቻ ሳይሆን እናቱም እንደምትነሣ በእውነት ተነበየ።
#ኋላ ጻድቃን የሚቆሙትን የቀኝ ቁመት እመቤታችን ዛሬ ቆማዋለች።"በወርቅ ልብስ ተሸፋፍና ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንዳለ አባቷ ቅዱስ ዳዊት።
#ልጇ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ኋላ ለጻድቃን የሚያወርሳቸውን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን" (1ኛ ቆሮ 2:9) ዛሬ ለእናቱ አውርሷታል።
ለነገሩ ራሷ መንግሥተ ሰማያት ናት።ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ንጉሠ ሰማያት ወምድር ማኅፀኗን መናገሻ አድርጎ ነግሦባታልና።
#ልጇ "ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።"(ዮሐ14:3) እንዳለ እርሷም እርሷ ባለችበት እንሆን ዘንድ ከልጇ ታማልደናለች።ማርያም ማለት መርኅ ለመንግሥተ ሰማያት (በቃልኪዳኗ በአማላጅነቷ ረድታ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ) ማለት ነውና።
#ጌታ መጋቢት 27 በመስቀል ላይ ሞቶ መጋቢት 29 በሦስተኛው ቀን እንደተነሣ እመቤታችንም በጥር 21 ዐርፋ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ በነሐሴ 14 ቀን በጌቴሴማኒ ተቀብራ በነሐሴ 16 ቀን በክብር፣በይባቤ መላእክት ተነሥታ ዐርጋለች።
#አይ የሞተ አይነሣም ለምትሉ አባታችን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን በመንፈስ እንጠራዋለን "ነገር ግን ሰው፤ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም።"(1ኛ ቆሮ 15:35) ብሎ ይዘልፍናል።
#ተነሥቶ ወደ ሰማይ አይወጣም የሚል ቢኖር ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን በሃይማኖት እንጠራዋለን፤እንዴትም ወደ ሰማይ እንደወጣ እንጠይቀዋለን።"ሲሄዱም እያዘገሙም ሲጫወቱ፤ እነሆ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።”(2ኛ ነገ 2:11)
ሞቶ ተነሥቶ ያረገ የለም የሚል ማንም ቢኖር ዳግመኛ ቅዱስ ጳውሎስ
"ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፤ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።"(1ኛ ተሰ 4:16-17) ሲል ይነግርልናል።
#አስተውሉ ያቀረብነው ማስረጃ ጻድቃንን የሚመለከት ነው።ጻድቃን እንዲህ ከከበሩ የጻድቃን እናታቸው የአምላክ እናት ቅደስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምማ ክብሯ ምን ያህል ይሆን !!!!!!!!???
እኛስ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም "አሕዛብ ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናመስግናት" እንላለን!!!
ነሐሴ ኪዳነምሕረት 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ኋላ ጻድቃን የሚቆሙትን የቀኝ ቁመት እመቤታችን ዛሬ ቆማዋለች።"በወርቅ ልብስ ተሸፋፍና ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንዳለ አባቷ ቅዱስ ዳዊት።
#ልጇ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ኋላ ለጻድቃን የሚያወርሳቸውን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን" (1ኛ ቆሮ 2:9) ዛሬ ለእናቱ አውርሷታል።
ለነገሩ ራሷ መንግሥተ ሰማያት ናት።ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ንጉሠ ሰማያት ወምድር ማኅፀኗን መናገሻ አድርጎ ነግሦባታልና።
#ልጇ "ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።"(ዮሐ14:3) እንዳለ እርሷም እርሷ ባለችበት እንሆን ዘንድ ከልጇ ታማልደናለች።ማርያም ማለት መርኅ ለመንግሥተ ሰማያት (በቃልኪዳኗ በአማላጅነቷ ረድታ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ) ማለት ነውና።
#ጌታ መጋቢት 27 በመስቀል ላይ ሞቶ መጋቢት 29 በሦስተኛው ቀን እንደተነሣ እመቤታችንም በጥር 21 ዐርፋ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ በነሐሴ 14 ቀን በጌቴሴማኒ ተቀብራ በነሐሴ 16 ቀን በክብር፣በይባቤ መላእክት ተነሥታ ዐርጋለች።
#አይ የሞተ አይነሣም ለምትሉ አባታችን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን በመንፈስ እንጠራዋለን "ነገር ግን ሰው፤ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም።"(1ኛ ቆሮ 15:35) ብሎ ይዘልፍናል።
#ተነሥቶ ወደ ሰማይ አይወጣም የሚል ቢኖር ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን በሃይማኖት እንጠራዋለን፤እንዴትም ወደ ሰማይ እንደወጣ እንጠይቀዋለን።"ሲሄዱም እያዘገሙም ሲጫወቱ፤ እነሆ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።”(2ኛ ነገ 2:11)
ሞቶ ተነሥቶ ያረገ የለም የሚል ማንም ቢኖር ዳግመኛ ቅዱስ ጳውሎስ
"ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፤ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።"(1ኛ ተሰ 4:16-17) ሲል ይነግርልናል።
#አስተውሉ ያቀረብነው ማስረጃ ጻድቃንን የሚመለከት ነው።ጻድቃን እንዲህ ከከበሩ የጻድቃን እናታቸው የአምላክ እናት ቅደስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምማ ክብሯ ምን ያህል ይሆን !!!!!!!!???
እኛስ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም "አሕዛብ ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናመስግናት" እንላለን!!!
ነሐሴ ኪዳነምሕረት 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
"ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር"
"የጻድቅ ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።"
መዝ 115:6
- የዛሬው በዓል ደግሞ ልዩ ነው።የጻድቁ አባት የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ፀሐይ የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ ዕረፍት ነውና!!!
- ለጻድቁ ክብርም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ክብርት ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን፣15ቱ ነቢያትን፣12ቱ ሐዋርያትን ብዙዎች የሰማይ ሠራዊትን ይዞ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደሚገኙበት የደብረ አስቦ ዋሻ ወርዶ ብዙ ቃልኪዳንን ሰጥቷቸዋል።
- የጻድቁስ ሐሳብ በሰማዕትነት አደባባይ ለክርስቶስ ፍቅር ደማቸውን አፍስሰው፣ሥጋቸው ተቆራርጦ፣አጥንታቸው ተከስክሶ ለማረፍ ነበር።በጣም የሚገርመው ይህንን ሐሳባቸውን ለጌታ የነገሩት የቀራቸው ምንም ዓይነት ተጋድሎ ሳይኖር ነበር።ነገር ግን ጌታ ጻድቁ ለእርሱ ያላቸውን ጽኑ ፍቅር ያውቃልና ምንም የቀራቸው እንደሌለና በከፍተኛ የሆድ ሕመም እንደሚያርፉ፤ይህንንም እንደ ስቅለቱና እንደ ሰማዕታት ደም እንደሚቆጥርላቸው ነግሯቸው በዚያ በክብር ዐርፈዋል።
- ዋሻዪቱን ሊነገርና ሊሰማ የማይችል ብርሃንና በዚህ ዓለም የሌለ የልዩ ልዩ የሽቱና የዕጣን መዓዛ ሞልቶባት፤ምድሪቱም እየተንቀጠቀጠች፤የሰማይ ሠራዊት ቅዱስ ዳዊት"ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና፤ በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።"ሲል እንደተናገረ (መዝ 41፥4) በክቡር ዳዊት ምስጋና“እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።”በማለት እያመሰኑ የጻድቁ ነፍስ ከሥጋቸው ተለየች።(መዝ 117፥24)
- ጌታችን የጻድቁን ነፍስ በክብር ተቀብሎ አቅፎ ሳማት።"የጸራሽ ንጽሕት ነፍስ ሆይ" ሲልም አመሰገናት።አባታችንን በሕይወተ ሥጋ ሳለ እንደነገራቸው በ15ቱ የገነትና በ5ቱ የመንግሥተ ሰማያት አህጉር ላይ ሾመው።አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል
“በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” ያለ አምላክ ለጻድቁ የመንፈስ ልጆች ይሆኑ ዘንድ በእነዚህ ሁሉ ላይ ሾመው።(ዮሐ 14፥2)
- በጻድቁ ስም ለተራበ ያበላ፤ለተጠማ ያጠጣ፤የየታረዘውን ያለበሰ፤ገድላቸውን የጻፈ ያጻፈ የሰማ፤ለቤተ ክርስቲያናቸው ዕጣን፣ዘቢብ፣ወይን፣ ሜሮን፣ንጹሕ ስንዴ ልዩ ልዩ መባዕ ያገባ፤ለበዓላቸው ለሚዘጋጀው ዝክር ውኃ በመቅዳት፣እንጨት በመፍለጥ፣ቅጠል በመቁረጥ የተራዳ፤በዓላቸውን ደስ ብሎት ያከበረ፤ከእነዚህ ሁሉ ባይቻለው በበዓላቸው ቀን የታመመ የጠየቀ ወይም ያዘነውን ያጽናና፤ በበዓላቸው ቀን ከ ቅዱስ ሥጋው ከክቡር ደሙ የተቀበለውን፤ይህንንም ባይችል ለበዓላቸው ከተዘጋጀው ዝክር የቀምሰ፤ከእነዚህ ሁሉ የተቻለውን አንዱን ቢፈጽም እንደሚምርላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
- ለቅዱሳኑ የሚሰጠውን ቃልኪዳን በተመለከተ ራሱ ጌታችን እንዲህ ሲል ተናግሯል"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ዋጋው አይጠፋበትም።"(ማቴ 10:40-42)
- የእግዚአብሔር የምሕረቱ ብዛት እንዴት ብዙና ጥልቅ ነው።ጻድቁን የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
ጻድቁም በጸሎታቸው በበረከታቸው ይጎብኙን፤በፍጹም ሰማያዊ መስቀላቸውም ይባርኩን፤በፍጹም ሰማያዊ ሥልጣነ ክህነታቸውም ከኃጢአት ማሠሪያ የተፈታን ንጹሐን ለመንግሥተ ሰማያትም የተዘጋጀን ድልዋን ያድርጉን!!! አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
ነሐሴ ተክለሃይማኖት/2016 ዓ.ም
"የጻድቅ ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።"
መዝ 115:6
- የዛሬው በዓል ደግሞ ልዩ ነው።የጻድቁ አባት የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ፀሐይ የአቡነ ተክለሃይማኖት በዓለ ዕረፍት ነውና!!!
- ለጻድቁ ክብርም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ክብርት ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን፣15ቱ ነቢያትን፣12ቱ ሐዋርያትን ብዙዎች የሰማይ ሠራዊትን ይዞ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደሚገኙበት የደብረ አስቦ ዋሻ ወርዶ ብዙ ቃልኪዳንን ሰጥቷቸዋል።
- የጻድቁስ ሐሳብ በሰማዕትነት አደባባይ ለክርስቶስ ፍቅር ደማቸውን አፍስሰው፣ሥጋቸው ተቆራርጦ፣አጥንታቸው ተከስክሶ ለማረፍ ነበር።በጣም የሚገርመው ይህንን ሐሳባቸውን ለጌታ የነገሩት የቀራቸው ምንም ዓይነት ተጋድሎ ሳይኖር ነበር።ነገር ግን ጌታ ጻድቁ ለእርሱ ያላቸውን ጽኑ ፍቅር ያውቃልና ምንም የቀራቸው እንደሌለና በከፍተኛ የሆድ ሕመም እንደሚያርፉ፤ይህንንም እንደ ስቅለቱና እንደ ሰማዕታት ደም እንደሚቆጥርላቸው ነግሯቸው በዚያ በክብር ዐርፈዋል።
- ዋሻዪቱን ሊነገርና ሊሰማ የማይችል ብርሃንና በዚህ ዓለም የሌለ የልዩ ልዩ የሽቱና የዕጣን መዓዛ ሞልቶባት፤ምድሪቱም እየተንቀጠቀጠች፤የሰማይ ሠራዊት ቅዱስ ዳዊት"ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና፤ በዓል የሚያደርጉ ሰዎች የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።"ሲል እንደተናገረ (መዝ 41፥4) በክቡር ዳዊት ምስጋና“እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።”በማለት እያመሰኑ የጻድቁ ነፍስ ከሥጋቸው ተለየች።(መዝ 117፥24)
- ጌታችን የጻድቁን ነፍስ በክብር ተቀብሎ አቅፎ ሳማት።"የጸራሽ ንጽሕት ነፍስ ሆይ" ሲልም አመሰገናት።አባታችንን በሕይወተ ሥጋ ሳለ እንደነገራቸው በ15ቱ የገነትና በ5ቱ የመንግሥተ ሰማያት አህጉር ላይ ሾመው።አስቀድሞ በቅዱስ ወንጌል
“በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤” ያለ አምላክ ለጻድቁ የመንፈስ ልጆች ይሆኑ ዘንድ በእነዚህ ሁሉ ላይ ሾመው።(ዮሐ 14፥2)
- በጻድቁ ስም ለተራበ ያበላ፤ለተጠማ ያጠጣ፤የየታረዘውን ያለበሰ፤ገድላቸውን የጻፈ ያጻፈ የሰማ፤ለቤተ ክርስቲያናቸው ዕጣን፣ዘቢብ፣ወይን፣ ሜሮን፣ንጹሕ ስንዴ ልዩ ልዩ መባዕ ያገባ፤ለበዓላቸው ለሚዘጋጀው ዝክር ውኃ በመቅዳት፣እንጨት በመፍለጥ፣ቅጠል በመቁረጥ የተራዳ፤በዓላቸውን ደስ ብሎት ያከበረ፤ከእነዚህ ሁሉ ባይቻለው በበዓላቸው ቀን የታመመ የጠየቀ ወይም ያዘነውን ያጽናና፤ በበዓላቸው ቀን ከ ቅዱስ ሥጋው ከክቡር ደሙ የተቀበለውን፤ይህንንም ባይችል ለበዓላቸው ከተዘጋጀው ዝክር የቀምሰ፤ከእነዚህ ሁሉ የተቻለውን አንዱን ቢፈጽም እንደሚምርላቸው ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።
- ለቅዱሳኑ የሚሰጠውን ቃልኪዳን በተመለከተ ራሱ ጌታችን እንዲህ ሲል ተናግሯል"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ዋጋው አይጠፋበትም።"(ማቴ 10:40-42)
- የእግዚአብሔር የምሕረቱ ብዛት እንዴት ብዙና ጥልቅ ነው።ጻድቁን የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
ጻድቁም በጸሎታቸው በበረከታቸው ይጎብኙን፤በፍጹም ሰማያዊ መስቀላቸውም ይባርኩን፤በፍጹም ሰማያዊ ሥልጣነ ክህነታቸውም ከኃጢአት ማሠሪያ የተፈታን ንጹሐን ለመንግሥተ ሰማያትም የተዘጋጀን ድልዋን ያድርጉን!!! አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
ነሐሴ ተክለሃይማኖት/2016 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
❤"የእግዚአብሔር መልአክ"❤
#በስሙ ስመ እግዚአብሔርን የተሸከመ መልአክ ማለት ነው።ሚካኤል፣ገብርኤል፣ሩፋኤል ወ.ዘ.ተ የሚሉት ስሞች ውስጥ "ኤል" የሚለው ቃል አምላክ ማለት ነውና።“ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ።”ዘጸ 23፥21
እንዲል።
#በልቡ ስብሐተ እግዚአብሔርን የያዘ በአንደበቱም
እግዚአብሔርን የሚያመሰግን መልአክ ነው።“አንዱም ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር።”(ኢሳ 6፥3) እንዳለ ነቢዩ።
#ፈቃደ እግዚአብሔርን የሚፈጽም ማለት ነው።ማር ያለውን ይምራል ፤ ቅሰፍ ያለውን ይቀስፋልና።
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”(መዝ33፥7)
“ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ።”ሐዋ12፥23
ተብሎ እንደተጻፈ።
#የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጥ መልአክ ነው።“ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።” (መዝ 18፥1) በሚለው ኃይለ ቃል ውስጥ "ሰማያት" የሚለው ቃል በምሥጢር መላእክት ማለት ነው።ይኸውም “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”
(ሉቃ2፥14) ባለው ኃይለ ቃል ውስጥ ካለው "አርያም" ከሚለው ቃል ጋር አንድ ነው።
#የእግዚአብሔርን ሕዝብ መርቶ ወደ ተዘጋጀላቸው ስፍራ የሚያገባ መልአክ ነው።“በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።”
( ዘጸ 23፥20) እንዲል።
#በእግዚአብሔር የሚታመነውን ሰው እግሩ በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቹ የሚያነሣ መልአክ ነው።"በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
(መዝ 90:11-12)
#ሰዎች ሁሉ መዳንን (መንግሥተ እግዚአብሔርን) እንዲወርሱ ለማገዝ የሚላክ፤የሚያገለግልም መልአክ ነው።“ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?”(ዕብ 1፥14) እንዳለ ሐዋርያው።
#በኃጢአተኞች መዳንም የሚደሰት መልአክ ማለት ነው።“ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።”ሉቃ15፥10
ይኸውም ሰውን እጅግ እጅግ እጅግ የሚወድድ መልአከ ምሕረት፣መልአከ ፍስሐ፣መልአከ ሰላም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነው!!!በረከቱ ይደርብን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር ሚካኤል/2017 ዓ.ም
#በስሙ ስመ እግዚአብሔርን የተሸከመ መልአክ ማለት ነው።ሚካኤል፣ገብርኤል፣ሩፋኤል ወ.ዘ.ተ የሚሉት ስሞች ውስጥ "ኤል" የሚለው ቃል አምላክ ማለት ነውና።“ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ።”ዘጸ 23፥21
እንዲል።
#በልቡ ስብሐተ እግዚአብሔርን የያዘ በአንደበቱም
እግዚአብሔርን የሚያመሰግን መልአክ ነው።“አንዱም ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር።”(ኢሳ 6፥3) እንዳለ ነቢዩ።
#ፈቃደ እግዚአብሔርን የሚፈጽም ማለት ነው።ማር ያለውን ይምራል ፤ ቅሰፍ ያለውን ይቀስፋልና።
“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።”(መዝ33፥7)
“ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ።”ሐዋ12፥23
ተብሎ እንደተጻፈ።
#የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጥ መልአክ ነው።“ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል።” (መዝ 18፥1) በሚለው ኃይለ ቃል ውስጥ "ሰማያት" የሚለው ቃል በምሥጢር መላእክት ማለት ነው።ይኸውም “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”
(ሉቃ2፥14) ባለው ኃይለ ቃል ውስጥ ካለው "አርያም" ከሚለው ቃል ጋር አንድ ነው።
#የእግዚአብሔርን ሕዝብ መርቶ ወደ ተዘጋጀላቸው ስፍራ የሚያገባ መልአክ ነው።“በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።”
( ዘጸ 23፥20) እንዲል።
#በእግዚአብሔር የሚታመነውን ሰው እግሩ በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቹ የሚያነሣ መልአክ ነው።"በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
(መዝ 90:11-12)
#ሰዎች ሁሉ መዳንን (መንግሥተ እግዚአብሔርን) እንዲወርሱ ለማገዝ የሚላክ፤የሚያገለግልም መልአክ ነው።“ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?”(ዕብ 1፥14) እንዳለ ሐዋርያው።
#በኃጢአተኞች መዳንም የሚደሰት መልአክ ማለት ነው።“ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።”ሉቃ15፥10
ይኸውም ሰውን እጅግ እጅግ እጅግ የሚወድድ መልአከ ምሕረት፣መልአከ ፍስሐ፣መልአከ ሰላም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነው!!!በረከቱ ይደርብን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር ሚካኤል/2017 ዓ.ም
❤ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ❤ (መዝ103፥27)
#ፍጥረት ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል።ምርጫ አይደለም የህልውና ጉዳይ እንጂ።በደመነፍስ ሕያዋን ሆነው የሚኖሩት እንስሳት፣አራዊት፣አዋዕፍ፣ዓሦችና አንበሪዎች እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ ተስፋ ያደርጉታል።እርሱም ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸዋል።ከቸር እጆቹ ጠግበው ያመሰግኑታል።
#ሰውም እንደ መላእክት ሁሉ "ተስፋ" የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።ተስፋውም በሕግ ቃልኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው።“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።”(ዘፍ 2፥17) ሲል ጌታ ለሰው ማዘዙ የሰው የሕይወት ተስፋው ሕጉን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዳል።
#ኋላም በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት የተሰጠው “ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።” (ዘጸ 20፥6) የሚለው ቃል ከላይ ያነሣነውን ሐሳብ ያጠናክረዋል።
#በእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተወደደ ሰው የሚባል ፍጡር ለሕይወቱ የተሰጠውን ሕግ አፍርሶ ቢበድል እንኳን ይቅር የመባል ተስፋ አለው። ስለዚህ የሚተማመነው "በእግዚአብሔር ምሕረት" ላይ እንጂ በራሱ ሕግ የመጠበቅ ብቃት ላይ አይሆንም።
#ተስፋ ቆርጫለሁ
#የሚለው ድምፅ እዚህና እዚያ ይሰማል።ተስፋ ማለት እግዚአብሔር ከሆነ ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት እግዚአብሔርን ትቼአለሁ ማለት ይሆናል።ተስፋ ለመቁረጥ ተስፋ ማድረግ ያስፈልጋል።ሰው ተስፋ የሚያደርጋቸው ጊዜአዊ ነገሮች ከእውነተኛ ተስፋው ከእግዚአብሔር ጋር ይምታቱበትና፤ያልተሳኩ እንደሆነ
ተስፋ ቆረጥሁ ይላል።መማርን፣አንድ ቦታ ተቀጥሮ መሥራትን፣እገሌን ወይ እገሊትን ማግባትን፣ልጆች መውለድን፣ባህር ማዶ ተሻግሮ መኖርን ወ.ዘ.ተ።
#አሁንስ ደከመኝ፣ታከትኩ፣ከዚህ በላይስ አልሄድም፣
በቃኝ ... የሚሉ ንግግሮች ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች አለመሳካት የሚነገሩ ናቸው።"እናንተ ስለፈለጋችሁ የሚሆን ነገር የለም፤ሆኑ አልሆኑ የእግረ መንገድ ጉዳዮች ናቸው።እነዚህ ጉዳዮች እንደ ሕፃናት ማቆያዎች (Day cares) ናቸው።የተፈጠራችሁላቸው ዓላማዎች አይደሉም።" እያለ ሕፃንነታችንን እየነገረን ከሆነስ!? "ፈቃድህ ይሁን" ብለን በፈቃዱ ሲከለክለን ማዘን አይገባም።
#ኑሮው!!! ኧረ ውድነቱ!!! "እግዚአብሔር ሆይ ወዴት ነህ???" "አንተን በማኖር ግብር ነኝ" ይልሃላ።ወይ ግሩም እስከዛሬ ታዲያ በኑሮ ርካሽነት ነበር እንዴ የኖርነው!?በእኔ ዕድሜ ሳውቅ በየጊዜው "ኑሮ ተወደደ" ነው የሚባለው።ሲወደድ እንጂ ሲረክስ ያየሁት ነገር የለም (ከሰው(ከእኔ) በቀር 😭)።ግን በቸርነቱ አለን!!!ግሩም ነው መቼስ!!!
#ለነፍሳችን ለማደር ከኃጢአት ጋር በምናደርገው ትግልም ተመሳሳዩ ነገር ይገጥመናል።"ከዚህ በኋላ ይህንን ያህል በድለህ እግዚአብሔር ይቅር የሚልህ መሰለህ" የሚል ሐሳብ በኅሊናህ ሲመጣ "አዎን ይቅር ይለኛል" በለው።ገድለህ "አዎን"፤አመንዝረህ "አዎን"፤ዘሙተህ "አዎን"፤ሰርቀህ "አዎን"፤"ዋሽተህ" አዎን!!!
#ታዲያ የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?
#ቅዱስ ዳዊት “መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም።”(መዝ 76፥19) ሲል የእግዚአብሔር አሠረ ፍትሑ (የፍርዱ መንገድ) እንደማይታወቅ ተናግሯል።ቅዱስ ጳውሎስም “የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።”(ሮሜ 11 ፥ 33) በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ አይመረመሬነት ገልጧል።ስለዚህ "የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "በራሱ ዘንድ ነው" የሚል ነው።
#ይህንን ሁሉ አጥፈተህማ እግዚአብሔር ሳይቀጣህ አይቀርም" የሚል ድምፅ ኅሊናህ ውስጥ ሲመላለስ፤"እግዚአብሔር ደግ አባቴ ነውና በደንብ ይቅጣኝ፤አንዴ አይደለም መቶ ጊዜ ይቅጣኝ።ብቻ ለአንተ ለከይሲው አሳልፎ አይሰጠኝ።እንኳን የእኔ የአንዱ በደል ከአዳም ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚሠራው ኃጢአት የደጉ አባቴን የእግዚአብሔርን አንዲቱን የምሕረት ጠብታ አያህልም!!!" በለው። እንዲህ ብለን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እግዚአብሔር ደስ ይለዋል።ቁጣውን ሁሉ ይተወዋል።ሰው ራሱ ላይ ከልቡ ሲፈርድ እግዚአብሔር ፍርዱን ይተውለታል!!!
“እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ ጽድቅንም ይወድዳል፤ ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።”(መዝ 11፥7) እንዳለ መዝሙረኛው በጽድቅ ራሳችን ላይ ፈርደን፤በልብ ቅንነት ራሳችንን ጻድቅ ለሆነ እግዚአብሔር ስንሰጥ፤እግዚአብሔር ደግሞ የምሕረት ፊቱን ያሳየናል።ይህንንም በልባችን በሚመላብን ፍጹም ሰላምና ደስታ እናውቃለን!!!
"#ሳለ #መድኃኔዓለም" የምወዳት የእናቶቼ ብሂል ናት።እውነትም "#ሳለ #መድኃኔዓለም" #አምላከ #ተክለሃይማኖት!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 13/2017 ዓ.ም
#ፍጥረት ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል።ምርጫ አይደለም የህልውና ጉዳይ እንጂ።በደመነፍስ ሕያዋን ሆነው የሚኖሩት እንስሳት፣አራዊት፣አዋዕፍ፣ዓሦችና አንበሪዎች እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ ተስፋ ያደርጉታል።እርሱም ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸዋል።ከቸር እጆቹ ጠግበው ያመሰግኑታል።
#ሰውም እንደ መላእክት ሁሉ "ተስፋ" የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።ተስፋውም በሕግ ቃልኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው።“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።”(ዘፍ 2፥17) ሲል ጌታ ለሰው ማዘዙ የሰው የሕይወት ተስፋው ሕጉን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዳል።
#ኋላም በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት የተሰጠው “ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።” (ዘጸ 20፥6) የሚለው ቃል ከላይ ያነሣነውን ሐሳብ ያጠናክረዋል።
#በእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተወደደ ሰው የሚባል ፍጡር ለሕይወቱ የተሰጠውን ሕግ አፍርሶ ቢበድል እንኳን ይቅር የመባል ተስፋ አለው። ስለዚህ የሚተማመነው "በእግዚአብሔር ምሕረት" ላይ እንጂ በራሱ ሕግ የመጠበቅ ብቃት ላይ አይሆንም።
#ተስፋ ቆርጫለሁ
#የሚለው ድምፅ እዚህና እዚያ ይሰማል።ተስፋ ማለት እግዚአብሔር ከሆነ ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት እግዚአብሔርን ትቼአለሁ ማለት ይሆናል።ተስፋ ለመቁረጥ ተስፋ ማድረግ ያስፈልጋል።ሰው ተስፋ የሚያደርጋቸው ጊዜአዊ ነገሮች ከእውነተኛ ተስፋው ከእግዚአብሔር ጋር ይምታቱበትና፤ያልተሳኩ እንደሆነ
ተስፋ ቆረጥሁ ይላል።መማርን፣አንድ ቦታ ተቀጥሮ መሥራትን፣እገሌን ወይ እገሊትን ማግባትን፣ልጆች መውለድን፣ባህር ማዶ ተሻግሮ መኖርን ወ.ዘ.ተ።
#አሁንስ ደከመኝ፣ታከትኩ፣ከዚህ በላይስ አልሄድም፣
በቃኝ ... የሚሉ ንግግሮች ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች አለመሳካት የሚነገሩ ናቸው።"እናንተ ስለፈለጋችሁ የሚሆን ነገር የለም፤ሆኑ አልሆኑ የእግረ መንገድ ጉዳዮች ናቸው።እነዚህ ጉዳዮች እንደ ሕፃናት ማቆያዎች (Day cares) ናቸው።የተፈጠራችሁላቸው ዓላማዎች አይደሉም።" እያለ ሕፃንነታችንን እየነገረን ከሆነስ!? "ፈቃድህ ይሁን" ብለን በፈቃዱ ሲከለክለን ማዘን አይገባም።
#ኑሮው!!! ኧረ ውድነቱ!!! "እግዚአብሔር ሆይ ወዴት ነህ???" "አንተን በማኖር ግብር ነኝ" ይልሃላ።ወይ ግሩም እስከዛሬ ታዲያ በኑሮ ርካሽነት ነበር እንዴ የኖርነው!?በእኔ ዕድሜ ሳውቅ በየጊዜው "ኑሮ ተወደደ" ነው የሚባለው።ሲወደድ እንጂ ሲረክስ ያየሁት ነገር የለም (ከሰው(ከእኔ) በቀር 😭)።ግን በቸርነቱ አለን!!!ግሩም ነው መቼስ!!!
#ለነፍሳችን ለማደር ከኃጢአት ጋር በምናደርገው ትግልም ተመሳሳዩ ነገር ይገጥመናል።"ከዚህ በኋላ ይህንን ያህል በድለህ እግዚአብሔር ይቅር የሚልህ መሰለህ" የሚል ሐሳብ በኅሊናህ ሲመጣ "አዎን ይቅር ይለኛል" በለው።ገድለህ "አዎን"፤አመንዝረህ "አዎን"፤ዘሙተህ "አዎን"፤ሰርቀህ "አዎን"፤"ዋሽተህ" አዎን!!!
#ታዲያ የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?
#ቅዱስ ዳዊት “መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም።”(መዝ 76፥19) ሲል የእግዚአብሔር አሠረ ፍትሑ (የፍርዱ መንገድ) እንደማይታወቅ ተናግሯል።ቅዱስ ጳውሎስም “የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።”(ሮሜ 11 ፥ 33) በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ አይመረመሬነት ገልጧል።ስለዚህ "የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "በራሱ ዘንድ ነው" የሚል ነው።
#ይህንን ሁሉ አጥፈተህማ እግዚአብሔር ሳይቀጣህ አይቀርም" የሚል ድምፅ ኅሊናህ ውስጥ ሲመላለስ፤"እግዚአብሔር ደግ አባቴ ነውና በደንብ ይቅጣኝ፤አንዴ አይደለም መቶ ጊዜ ይቅጣኝ።ብቻ ለአንተ ለከይሲው አሳልፎ አይሰጠኝ።እንኳን የእኔ የአንዱ በደል ከአዳም ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚሠራው ኃጢአት የደጉ አባቴን የእግዚአብሔርን አንዲቱን የምሕረት ጠብታ አያህልም!!!" በለው። እንዲህ ብለን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እግዚአብሔር ደስ ይለዋል።ቁጣውን ሁሉ ይተወዋል።ሰው ራሱ ላይ ከልቡ ሲፈርድ እግዚአብሔር ፍርዱን ይተውለታል!!!
“እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ ጽድቅንም ይወድዳል፤ ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።”(መዝ 11፥7) እንዳለ መዝሙረኛው በጽድቅ ራሳችን ላይ ፈርደን፤በልብ ቅንነት ራሳችንን ጻድቅ ለሆነ እግዚአብሔር ስንሰጥ፤እግዚአብሔር ደግሞ የምሕረት ፊቱን ያሳየናል።ይህንንም በልባችን በሚመላብን ፍጹም ሰላምና ደስታ እናውቃለን!!!
"#ሳለ #መድኃኔዓለም" የምወዳት የእናቶቼ ብሂል ናት።እውነትም "#ሳለ #መድኃኔዓለም" #አምላከ #ተክለሃይማኖት!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 13/2017 ዓ.ም
#ተስፋ ነቢያት ክርስቶስ
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
#ተስፋ ነቢያት ክርስቶስ
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።
#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።
#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።
#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!
#መልካም ጾመ ነቢያት
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
❤ሥላሴ❤
#ከቸርነትህ እጅግ እጅግ እጅግ ጥቂቱን ልበል ፦
#ሥላሴ ጌታዬ አምላኬም❤
#ሥላሴ አባቴ እናቴም❤
#ሥላሴ የጠላትን ጦር መመከቻ ጋሻዬ❤
#ሥላሴ ጠላትን ማጥቂያ ጦሬ❤
#ሥላሴ ከኃዘኔ መጽናኛ ደስታዬ❤
#ሥላሴ በድካሜ ጊዜ ጉልበቴና ኃይሌ❤
#ሥላሴ የተቆረጠውን የምትቀጥል ተስፋዬ❤
#ሥላሴ ሳዝን ሲከፋኝ ማልቀሻዬ❤
#ሥላሴ ሩኅሩኅ የጽድቅ ዳኛዬ❤
#ሥላሴ ሃይማኖቴ ማዕተቤም❤
+ኃይልየ #ሥላሴ ወጸወንየ #ሥላሴ
+በስመ #ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ
+ ሁሉ #ከሥላሴ #በሥላሴ #ለሥላሴ ሆነ !!!
+ክብር #ለሥላሴ በሰማይ በምድር!!! +በባሕርና በጥልቆች ሁሉ ይሁን አሜን!!!
ታኅሣሥ #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ከቸርነትህ እጅግ እጅግ እጅግ ጥቂቱን ልበል ፦
#ሥላሴ ጌታዬ አምላኬም❤
#ሥላሴ አባቴ እናቴም❤
#ሥላሴ የጠላትን ጦር መመከቻ ጋሻዬ❤
#ሥላሴ ጠላትን ማጥቂያ ጦሬ❤
#ሥላሴ ከኃዘኔ መጽናኛ ደስታዬ❤
#ሥላሴ በድካሜ ጊዜ ጉልበቴና ኃይሌ❤
#ሥላሴ የተቆረጠውን የምትቀጥል ተስፋዬ❤
#ሥላሴ ሳዝን ሲከፋኝ ማልቀሻዬ❤
#ሥላሴ ሩኅሩኅ የጽድቅ ዳኛዬ❤
#ሥላሴ ሃይማኖቴ ማዕተቤም❤
+ኃይልየ #ሥላሴ ወጸወንየ #ሥላሴ
+በስመ #ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ
+ ሁሉ #ከሥላሴ #በሥላሴ #ለሥላሴ ሆነ !!!
+ክብር #ለሥላሴ በሰማይ በምድር!!! +በባሕርና በጥልቆች ሁሉ ይሁን አሜን!!!
ታኅሣሥ #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ደስ ይበልሽ#
-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።
-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።
- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።
- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።
"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)
- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።
-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"
-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።
#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!
-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።
-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።
- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።
- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።
"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)
- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።
-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"
-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።
#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!
-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
❤ከዕለቱ #መዝሙር❤
#መዝሙረ ዳዊት 69
አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።
እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!
#ታኅሣሥ 23/2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#መዝሙረ ዳዊት 69
አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።
እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!
#ታኅሣሥ 23/2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
“#ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ ስለ ጠላትህ፥ ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት።”(መዝ 8፥2)
#ፍስሐ #ጽዮን የተባለ #ተክለሃይማኖት በተወለደ በሦስተኛው ቀን "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ እግዚአብሔርን አመሰገነ።
#ነቢየ #እግዚአብሔር #ኤርምያስ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።” (ኤር 1፥5)እንደተባለ ቅዱስ #ተክለሃይማኖት ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ነቢይ ሆኖ ለእግዚአብሔር ተለየ።
#መልአከ #ብርሃን ቅዱስ #ገብርኤል ስለ ቅዱስ #ዮሐንስ መጥምቅ“በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤”( ሉቃስ 1፥15) እንዳለ #ተክለሃይማኖት ጻድቅ ከዓለምና ከምኞቷ ሁሉ የተለየ ፤ በጌታም ፊት ታላቅ የተባለ ፤ መንፈስ ቅዱስም የሞላበት ነው።ዳግመኛም መልአክ “ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”(ሉቃ 1፥14) እንዳለ በፍስሐ ጽዮን (በጽዮን ደስታ) በ #ተክለሃይማኖት መወለድ ለጊዜው አባቱ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና እናቱ ቅድስት #እግዚእ ኃረያ ተደስተዋል ፤ ለፍጻሜው ግን ጽዮን የተባለች ቅድስት #ቤተክርስቲያን ተደስታለች።
#ቅዱስ #ጳውሎስም ስለ ራሱ “ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም”(ገላ1፥15-16) እንዳለ አባታችን #ተክለሃይማኖት በጸጋ #መንፈስ #ቅዱስ ለስብከተ ወንጌል ገና በማኅፀን ተጠራ።
#ጌታም በወንጌል ስለ እነ #ተክለሃይማኖት እንዲህ አለ “በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ”(ማቴ 19፥12)
#እንኳን አደረሳችሁ!!!
#ታኅሣሥ 26 /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ፍስሐ #ጽዮን የተባለ #ተክለሃይማኖት በተወለደ በሦስተኛው ቀን "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ እግዚአብሔርን አመሰገነ።
#ነቢየ #እግዚአብሔር #ኤርምያስ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።” (ኤር 1፥5)እንደተባለ ቅዱስ #ተክለሃይማኖት ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ነቢይ ሆኖ ለእግዚአብሔር ተለየ።
#መልአከ #ብርሃን ቅዱስ #ገብርኤል ስለ ቅዱስ #ዮሐንስ መጥምቅ“በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤”( ሉቃስ 1፥15) እንዳለ #ተክለሃይማኖት ጻድቅ ከዓለምና ከምኞቷ ሁሉ የተለየ ፤ በጌታም ፊት ታላቅ የተባለ ፤ መንፈስ ቅዱስም የሞላበት ነው።ዳግመኛም መልአክ “ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”(ሉቃ 1፥14) እንዳለ በፍስሐ ጽዮን (በጽዮን ደስታ) በ #ተክለሃይማኖት መወለድ ለጊዜው አባቱ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና እናቱ ቅድስት #እግዚእ ኃረያ ተደስተዋል ፤ ለፍጻሜው ግን ጽዮን የተባለች ቅድስት #ቤተክርስቲያን ተደስታለች።
#ቅዱስ #ጳውሎስም ስለ ራሱ “ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም”(ገላ1፥15-16) እንዳለ አባታችን #ተክለሃይማኖት በጸጋ #መንፈስ #ቅዱስ ለስብከተ ወንጌል ገና በማኅፀን ተጠራ።
#ጌታም በወንጌል ስለ እነ #ተክለሃይማኖት እንዲህ አለ “በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ”(ማቴ 19፥12)
#እንኳን አደረሳችሁ!!!
#ታኅሣሥ 26 /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ከሕግ በላይ ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ንጽሕት ነሽ።ከአንቺ በቀር መርገመ አዳም ወሔዋን የቀረለት የለምና።
#ከሕግ በላይ ጌታን በድንግልና ፀንሰሽ በድንግልና ወለድሽ።ድንግልም እናትም ሆንሽ፤ያውም ወላዲተ አምላክ
#ከሕግም ውጪ መርገም ሳያገኝሽ ኃጢአት ሳይኖርብሽ ሞትን ቀመስሽ።ሞት የኃጢአት ውጤት ነውና!!!
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ #ለማርያም የዐፅብ ለኩሉ"
"ሞትስ ለሟች ይገባል ፤ #የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል"
#ኃጢአትን ሳይሠሩ ሞትን መቅመስ(ሞተ ሥጋም ቢሆን በቀደመው በደል የመጣ ነውና) ፤ ደግሞ ኃጢአትን ሠርቶ #በእመቤታችን የዕረፍት ቃልኪዳን ተማምኖ ዝክር አድርጎ ከዳግም ሞት መዳን!!!
#የእግዚአብሔር ፍርዱ ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!
#የእመቤታችን በረከቷ ይደርብን፤ፍቅሯ አይለየን!!!
#አስተርእዮ #ማርያም / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ከሕግ በላይ ጌታን በድንግልና ፀንሰሽ በድንግልና ወለድሽ።ድንግልም እናትም ሆንሽ፤ያውም ወላዲተ አምላክ
#ከሕግም ውጪ መርገም ሳያገኝሽ ኃጢአት ሳይኖርብሽ ሞትን ቀመስሽ።ሞት የኃጢአት ውጤት ነውና!!!
"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ #ለማርያም የዐፅብ ለኩሉ"
"ሞትስ ለሟች ይገባል ፤ #የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል"
#ኃጢአትን ሳይሠሩ ሞትን መቅመስ(ሞተ ሥጋም ቢሆን በቀደመው በደል የመጣ ነውና) ፤ ደግሞ ኃጢአትን ሠርቶ #በእመቤታችን የዕረፍት ቃልኪዳን ተማምኖ ዝክር አድርጎ ከዳግም ሞት መዳን!!!
#የእግዚአብሔር ፍርዱ ምን ይደንቅ! ምን ይረቅ!
#የእመቤታችን በረከቷ ይደርብን፤ፍቅሯ አይለየን!!!
#አስተርእዮ #ማርያም / 2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ዛሬ የኪዳናት ሁሉ ፍጻሜ #ኪዳነ #ምሕረት ናት።ለቅዱሳኑ ለአዳም፣ለኖኅ፣ለመልከጼዲቅ፣ለአብር
ሃም፣ለዳዊት የተገባው ቃልኪዳን ሁሉ በእግዝእትነ ድንግል ማርያም ፍጻሜውን አገኘ።ይህ ኪዳነ እግዚአብሔር ምንድነው? ቢሉ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆን ነው።ሰው ሆኖም መዳናችንን መፈጸም ነው።
#ቅዱስ ዳዊት “ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።” መዝ 3፥8
ብሎ እንደተናገረው ሰውን ከተፈረደበት የሞት ፍርድ ማዳን የሚቻለው የፈረደበት እግዚአብሔር ነው።
#“ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል፤ የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።”(መዝ 33፥5) በሚለው ቃልም ምን እግዚአብሔር ሰውን ማዳን(ጽድቅ) ቢችልም ፍርድንም ይወድዳል።ሰውን በቸርነቱ የማዳን ፈቃዱ ጽድቅ ሲሆን፤የበደለ ሰው ነውና ሊክስ የሚገባውም ሰው ነው፦ይህ ፍርድ ይባላል።
ሰው ደግሞ ራሱ የሞት ፍርድ ስላለበት ሰውን ማዳን የማይቻለው ነው።ታዲያ ምን ተሻለ? የሞት ፍርድ የሌለበት፤የባሕርይ ጉስቁልና (fallen nature)፤መርገመ አዳም መርገመ ሔዋን ያላገኘው ንጹሕና ቅዱስ ሰው ነዋ !!! ይህንን ነቢዩ ኢሳይያስ
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።”
(ኢሳ1፥9) በማለት የገለጸው ከላይ ካነሣናቸው ጉዳዮች የቀረች ንጹሕ ዘር ታስፈልግ ነበር።ከዚህች ንጹሕ ዘር ነው ራሱ እግዚአብሔር የነሣውን ሥጋዋን ነፍሷን ተዋሕዶ የሚያድነን።
#ይህቺ አዳምና ሔዋን በበደሉት በደል ከመጣው ጣጣ ሁሉ ከአዳም ልጆች በተለየ መልኩ ያስቀራት ዘር እመቤታችን ናት።ልብ በሉ "ዘርን ባያስቀርልን" አለ እንጂ "ዘሮችን" አላለም።ዘርዪቱ አንዲት ናት።ልዩ ናት!!!አትደገምም፤አትነገርም።ይህቺ ሰዎች ሁሉ ላይ ከመጣው የሞት ዕዳ የቀረች (የተረፈች) ዘር እመቤታችን ለመሆኗ ሰማያውያን መላእክትን ምድራውያን ጻድቃንን ምስክር እናቆማለን።“እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ።”(ኢሳ 1፥2)
1.“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
(ዘፍ 3፥15) የሰማዮች ሰማይ እግዚአብሔር የተናገረው ቃል ነው።ይህቺ ከእባቡ (ከሰይጣን) ጋር ጠላትነት ውስጥ የምትገባ ዘር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።ሔዋን ከመሰለችህ ተሳስተሃል።ስለ እርሷማ ቅዱስ ኤፍሬም "ከይሲ ዲያቢሎስ ያሳታት ሔዋንን እግዚአብሔር ምጥሽንና ፃዕርሽን አበዛዋለሁ ብሎ ፈረደባት"ብሎ ተናገረ ።በምክረ ሰይጣን የተስማማ ሰው ከሰይጣን ጋር ጠላትነት ውስጥ ሊገባም አይችልም።ይህ የእመቤታችንና የሰይጣን ጠላትነት “ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ”
(ራእይ 12፥17) ተብሎ ተጽፎለታል።ዘንዶው ማንነው? ካልክ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።”(ራእይ 12፥9) በማለት የቀደመው እባብ (ሰይጣን) መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ ይነግርሃል።ሴቲቱስ?“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”ራእይ 12፥1
የተባላለት ድንግል ማርያም ናት።በዘፍጥረት በሴቲቱና በእባቡ ጠላትነት እንደሚደረግ እግዚአብሔር ነገረን።ቅዱስ ዮሐንስ ይህን ጠላትነት በተግባራዊ መልኩ በራእዩ አስረዳን።
2. “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።”(መዝ 45፥4) ልዑል እግዚአብሔር ማደሪያውን ለየ፤አመሰገነ፤አከበረ።
ቅዱስ እግዚአብሔር ማደሪያው የምትሆን ድንግል ማርያምን ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ጠበቀ ፤ በመጠበቁም አከበረ።
3.“ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።”ሉቃ1፥27
ቅዱስ ገብርኤል የተላከው "ከደናግል ወደ አንዲቱ" አይደለም፤ወደ "አንዲት ድንግል" እንጂ!!!በሥጋ ደናግል የሆኑ ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ።እነዚህ ግን እንደ ማንኛውም የሰው ዘር መርገመ አዳም ወሔዋን ደርሶባቸዋል።እመቤታችን ግን ከዚህ ሁሉ ንጽሕት ናትና "አንዲት ድንግል" አላት።"አንዲት ድንግል" ማለትም "ብቸኛዪቱ ድንግል" ማለት ነው።ይህ ዓይነቱ ድንግልና ነው "የድንግልናሽ ምስጋናና ክብር ታላቅ ነው" ተብሎ የተመሰገነ።
4. “መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።”(ሉቃ 1፥28)
ሰው ሁሉ ኃዘን አግኝቶት "ደስ ይበልሽ" የተባለች፤ሰው ሁሉ ከጸጋ እግዚአብሔር ጎድሎ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" ተብላ የተመሰገነች፤በበደል በደሉንም ተከትሎ በደረሰብን መርገም ከእግዚአብሔር ተለይተን በነበርን ጊዜ መርገምም ሆነ በደል ካላገኛት ከእመቤታችን ጋር ጌታ እግዚአብሔር ነበር።ከሌሎች ሴቶች መካከል የተባረከች ናት እመቤታችን።መባረክ የመረገም ተቃራኒ መሆኑ ግልጥ ነው።ሌሎች ሴቶች ላይ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።” (ዘፍ 3፥16) የተባለው መርገም ሲደርስባቸው በእመቤታችን ግን ይህ ሁሉ የለባትም።
#በእውኑ #የእመቤታችን ሥጋ የወደቀው የአዳም ሥጋ እንዳልሆነ፤አዳም ሳይበድል የነበረው ሥጋ እንደሆነ ዐወቅን ተረዳን!!!ይህንን የገለጠልን ለእመቤታችን የምሕረት ቃል ኪዳን የሰጠ ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
#የካቲት #ኪዳነ #ምሕረት /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
ሃም፣ለዳዊት የተገባው ቃልኪዳን ሁሉ በእግዝእትነ ድንግል ማርያም ፍጻሜውን አገኘ።ይህ ኪዳነ እግዚአብሔር ምንድነው? ቢሉ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆን ነው።ሰው ሆኖም መዳናችንን መፈጸም ነው።
#ቅዱስ ዳዊት “ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።” መዝ 3፥8
ብሎ እንደተናገረው ሰውን ከተፈረደበት የሞት ፍርድ ማዳን የሚቻለው የፈረደበት እግዚአብሔር ነው።
#“ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል፤ የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።”(መዝ 33፥5) በሚለው ቃልም ምን እግዚአብሔር ሰውን ማዳን(ጽድቅ) ቢችልም ፍርድንም ይወድዳል።ሰውን በቸርነቱ የማዳን ፈቃዱ ጽድቅ ሲሆን፤የበደለ ሰው ነውና ሊክስ የሚገባውም ሰው ነው፦ይህ ፍርድ ይባላል።
ሰው ደግሞ ራሱ የሞት ፍርድ ስላለበት ሰውን ማዳን የማይቻለው ነው።ታዲያ ምን ተሻለ? የሞት ፍርድ የሌለበት፤የባሕርይ ጉስቁልና (fallen nature)፤መርገመ አዳም መርገመ ሔዋን ያላገኘው ንጹሕና ቅዱስ ሰው ነዋ !!! ይህንን ነቢዩ ኢሳይያስ
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።”
(ኢሳ1፥9) በማለት የገለጸው ከላይ ካነሣናቸው ጉዳዮች የቀረች ንጹሕ ዘር ታስፈልግ ነበር።ከዚህች ንጹሕ ዘር ነው ራሱ እግዚአብሔር የነሣውን ሥጋዋን ነፍሷን ተዋሕዶ የሚያድነን።
#ይህቺ አዳምና ሔዋን በበደሉት በደል ከመጣው ጣጣ ሁሉ ከአዳም ልጆች በተለየ መልኩ ያስቀራት ዘር እመቤታችን ናት።ልብ በሉ "ዘርን ባያስቀርልን" አለ እንጂ "ዘሮችን" አላለም።ዘርዪቱ አንዲት ናት።ልዩ ናት!!!አትደገምም፤አትነገርም።ይህቺ ሰዎች ሁሉ ላይ ከመጣው የሞት ዕዳ የቀረች (የተረፈች) ዘር እመቤታችን ለመሆኗ ሰማያውያን መላእክትን ምድራውያን ጻድቃንን ምስክር እናቆማለን።“እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ።”(ኢሳ 1፥2)
1.“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
(ዘፍ 3፥15) የሰማዮች ሰማይ እግዚአብሔር የተናገረው ቃል ነው።ይህቺ ከእባቡ (ከሰይጣን) ጋር ጠላትነት ውስጥ የምትገባ ዘር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።ሔዋን ከመሰለችህ ተሳስተሃል።ስለ እርሷማ ቅዱስ ኤፍሬም "ከይሲ ዲያቢሎስ ያሳታት ሔዋንን እግዚአብሔር ምጥሽንና ፃዕርሽን አበዛዋለሁ ብሎ ፈረደባት"ብሎ ተናገረ ።በምክረ ሰይጣን የተስማማ ሰው ከሰይጣን ጋር ጠላትነት ውስጥ ሊገባም አይችልም።ይህ የእመቤታችንና የሰይጣን ጠላትነት “ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ”
(ራእይ 12፥17) ተብሎ ተጽፎለታል።ዘንዶው ማንነው? ካልክ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።”(ራእይ 12፥9) በማለት የቀደመው እባብ (ሰይጣን) መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ ይነግርሃል።ሴቲቱስ?“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”ራእይ 12፥1
የተባላለት ድንግል ማርያም ናት።በዘፍጥረት በሴቲቱና በእባቡ ጠላትነት እንደሚደረግ እግዚአብሔር ነገረን።ቅዱስ ዮሐንስ ይህን ጠላትነት በተግባራዊ መልኩ በራእዩ አስረዳን።
2. “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።”(መዝ 45፥4) ልዑል እግዚአብሔር ማደሪያውን ለየ፤አመሰገነ፤አከበረ።
ቅዱስ እግዚአብሔር ማደሪያው የምትሆን ድንግል ማርያምን ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ጠበቀ ፤ በመጠበቁም አከበረ።
3.“ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።”ሉቃ1፥27
ቅዱስ ገብርኤል የተላከው "ከደናግል ወደ አንዲቱ" አይደለም፤ወደ "አንዲት ድንግል" እንጂ!!!በሥጋ ደናግል የሆኑ ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ።እነዚህ ግን እንደ ማንኛውም የሰው ዘር መርገመ አዳም ወሔዋን ደርሶባቸዋል።እመቤታችን ግን ከዚህ ሁሉ ንጽሕት ናትና "አንዲት ድንግል" አላት።"አንዲት ድንግል" ማለትም "ብቸኛዪቱ ድንግል" ማለት ነው።ይህ ዓይነቱ ድንግልና ነው "የድንግልናሽ ምስጋናና ክብር ታላቅ ነው" ተብሎ የተመሰገነ።
4. “መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።”(ሉቃ 1፥28)
ሰው ሁሉ ኃዘን አግኝቶት "ደስ ይበልሽ" የተባለች፤ሰው ሁሉ ከጸጋ እግዚአብሔር ጎድሎ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" ተብላ የተመሰገነች፤በበደል በደሉንም ተከትሎ በደረሰብን መርገም ከእግዚአብሔር ተለይተን በነበርን ጊዜ መርገምም ሆነ በደል ካላገኛት ከእመቤታችን ጋር ጌታ እግዚአብሔር ነበር።ከሌሎች ሴቶች መካከል የተባረከች ናት እመቤታችን።መባረክ የመረገም ተቃራኒ መሆኑ ግልጥ ነው።ሌሎች ሴቶች ላይ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።” (ዘፍ 3፥16) የተባለው መርገም ሲደርስባቸው በእመቤታችን ግን ይህ ሁሉ የለባትም።
#በእውኑ #የእመቤታችን ሥጋ የወደቀው የአዳም ሥጋ እንዳልሆነ፤አዳም ሳይበድል የነበረው ሥጋ እንደሆነ ዐወቅን ተረዳን!!!ይህንን የገለጠልን ለእመቤታችን የምሕረት ቃል ኪዳን የሰጠ ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
#የካቲት #ኪዳነ #ምሕረት /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት" የዘወትር ጸሎታችን ነው።አስቀድሞ በማኅፀነ #ድንግል ሥጋችንን ቃል ስለተዋሐደው በባሕርይ አምላክነት (በፈጣሪነት) ዐርጓል (ከፍ ከፍ ብሏል)።ሆኖም ግን እስከ ትንሣኤ ድረስ የትሕትናን ሥራ ከልዕልና ጋር ሲሠራ ቆይቷል።ከትንሣኤ በኋላ እስከ ዐርባ ቀን ድረስ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ለቅዱሳን #ሐዋርያት ሲያስተምር ቆይቶ በአርባኛው ቀን በግርማና በስብሐት ወደ ሰማይ ዐረገ፤በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ።
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት" የዘወትር ጸሎታችን ነው።አስቀድሞ በማኅፀነ #ድንግል ሥጋችንን ቃል ስለተዋሐደው በባሕርይ አምላክነት (በፈጣሪነት) ዐርጓል (ከፍ ከፍ ብሏል)።ሆኖም ግን እስከ ትንሣኤ ድረስ የትሕትናን ሥራ ከልዕልና ጋር ሲሠራ ቆይቷል።ከትንሣኤ በኋላ እስከ ዐርባ ቀን ድረስ ምሥጢረ መንግሥተ ሰማያትን ለቅዱሳን #ሐዋርያት ሲያስተምር ቆይቶ በአርባኛው ቀን በግርማና በስብሐት ወደ ሰማይ ዐረገ፤በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ።
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም
አካላዊ ቃል ከድንግል #ማርያም ነሥቶ የተዋሐደው ሥጋ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነው ማለትም ምልዐትን፣ ስፋትን ፣ርቀትን የአብ ልጅነትን ገንዘብ ያደረገው ቃል ሥጋን በተዋሐደበት (ጌታ በተፀነሰበት) ቅጽበት ነው።ዳግመኛ በትሕትና ሥራ ላይገለጥ ከብሮ የታየበት በዓሉ ደግሞ ዕርገት ነው።
"ታስበው ዘንድ ሰው ምንድነው" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ባለ ክብር ሰውነታችንን ያከብር ዘንድ በእውነት እኛ ምንድነን?ዛሬ የእኛ ሰውነት በቅዱሳን በመላእክት ታጅቦ ወደ ሰማይ ወጣ።ድል ነሥቶ በአብ ቀኝ ተቀመጠ።
"በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ" ስንል ክርስቶስ ከአባቱ ቀኝ ተለይቶ ኖሮ ኋላ
ወደ አባቱ ቀኝ የሄደ አይደለም።ሰው የሆነበትን ዓላማ ፈጽሞ ሰይጣንን አሥሮ ሰውን ነፃ አውጥቶ በድል ነሺነት በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ ማለታችን ነው።
#ዕርገትን ስናስብ
#የእግዚአብሔርን ውለታ እናስባለን (እኛን ያከበረበትን ክብር)
#ያዘጋጀልንን መንግሥተ ሰማያት እናስባለን።ተስፋችን ይለመልማል።
“ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።”(ዮሐ 14፥3) "ሄጄም" ሲል ዕርገቱን ተናገረ።
#የዳግም ምጽአትን ፍርድን በማሰብ ራሳችንን እናዘጋጃለን።
“የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው #ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።”(ሐዋ 1፥11)
#በመንግሥተ ሰማያት የሚኖረንን ዕርገታዊ ሕይወት እናስባለን።
በክብር ላይ ክብር፣በጸጋ ላይ ጸጋ፣በጣዕም ላይ ጣዕም፣በመዓዛ ላይ መዓዛ በማያቋርጥ ከፍ ማለት መኖራችንን ተስፋ እናደርጋለን።
"የሙታንን መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ተስፋ እናደርጋለን" "የሚመጣው ሕይወት" ምንድንነው?ከትንሣኤ በኋላ የሚኖረን የማያቋርጥ ሱታፌ #አምላክ (#እግዚአብሔርን መምሰል) ነው እንጂ!!!
ከበዓለ ዕርገቱ ረድኤት በረከት ያሳትፈን!!
#ኢዮብ ክንፈ
ግንቦት 21/2017 ዓ.ም