ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
Forwarded from Eyob kinfe
"ሕይወትን በሚሰጥ አዳኝ በሆነ ከአብ በሠረጸ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን" (ጸሎተ ሃይማኖት)

#እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በዛሬው ዕለት በእሳትና በነፋስ ተመስሎ ለቅዱሳን ሐዋርያት ወረደ።ይኸውም በቅዱስ ማርቆስ እናት በማርያም ቤት የደስታ መፍሰሻ ወላዲተ አምላክን ከብበው በአንድ ልብ ሲጸልዩ ነው።

#ፍስሕት (ደስተኛዪቱን) ይዘው ቢጸልዩ የደስታ መንፈስ የሆነ መንፈስቅዱስ ወረደላቸው።

#መዝገበ ምሥጢር ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ከሣቴ ምሥጢር (ምሥጢርን የሚገልጥ) መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው።በዚህም በሚያውቁት አንድ ቋንቋ ላይ ሰባ አንድ ቋንቋ ተገልጦላቸው ቅዱስ ወንጌልን ሰብከዋል።

#ናዛዚት (የምታረጋጋ) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ናዛዚ (የሚያረጋጋ) መንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።

#ንጽሕት ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ) መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።

#ጽንዕት (የጸናች) ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ መጽንሒ (የሚያጸና) መንፈስቅዱስን ተቀበሉ።

#መስተሥርዪ ኃጢአት (ኃጢአትን ይቅር የምታስብል) ርኅርኂተ ኅሊና ድንግል ማርያምን ይዘው ቢጸልዩ ኃጢአትን ይቅር የሚል መንፈስ ቅዱስ በእሳት ተመስሎ ወደ እነርሱ መጣ።

#እናታቸውን ይዘው ምን ሊያጡ ኖሯል?ጽዮንን (እመቤታችንን) ከብበው ቢጸልዩ በደብረ ጽዮን የሚኖር መንፈስ ቅዱስ አደረባቸው።

#ይህቺ ቀን የቅድስት ቤተክርስቲያን የልደት ቀን ናት።ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው እንደ ጌታቸው ሁሉ ጾሙ ጸለዩ።መንፈስ ቅዱስ ያደረበት እንደሚጾም እንደሚጸልይ ያጠይቃል።በዓለም ሁሉ ዞረው ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ሰበኩ።

#አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቸርነቱ በእመቤታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት አማላጅነት ከመፍገምገም ወደ ጽናት ፣ ከኃዘን ወደ ደስታ ፣ ከኃጢአት ወደ ንጽሕና ፣ ከመቅበዝበዝ ወደ መረጋጋት ፣ ከድንቁርና ወደ ዕውቀት ይመልሰን!!! አሜን !!!

#በዓለ ጰራቅሊጦስ

ወርኃ ሰኔ 16 / 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ