ዐውደ ምሕረት
3.68K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#ተስፋ ነቢያት ክርስቶስ

#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።

#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።

#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።

#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!

#መልካም ጾመ ነቢያት

#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
#ተስፋ ነቢያት ክርስቶስ

#ከአዳም ጀምሮ የነበሩ ነቢያት ሁሉ ተስፋቸው
#ክርስቶስ ነው።#ክርስቶስም ዓለሙን ሁሉ ያዳነው መሲሕ ነው።ከድንግሊቱ እመቤታችን ማርያም ሲወለድም #ኢየሱስ" ተብሎ ተጠራ።በመሆኑም ነቢያት የተነበዩለት ክርስቶስ (መሲሑ) ከእመቤታችን የተወለደው #ኢየሱስ" ነው ለማለት "ኢየሱስ ክርስቶስ" ብለን እንጠራዋለን።"ኢየሱስ ክርስቶስ" ማለት "መድኃኒት ወንጉሥ" ማለትም ነው።

#የነቢያቱ ጾም ተስፋ ነው።ልደተ ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ የተስፋው ፍጻሜ።ከቅዱስ አዳም ጀምሮ 5,500 ዓመት ያህል የጌታ ልደቱ ተጠብቋል።"
“የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ”(ገላ 4፥4) እንዳለ ሐዋርያው እግዚአብሔር በአዳም ሥጋ ተገለጠ።

#ልዑል ክንዱን ሰደደልን" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም ልዑል አብ ክንዱን ወልድን ላከልን።በዚህም ተስፋችን
ተፈጸመ።እውነተኛ ተስፋ እንዲህ ደጅ ያስጠናል።በ ቀላሉም አይገኝም።በረጅሙ ጾመ ነቢያት “ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን አምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ”(ቲቶ 2፥12-13) አየን።

#በሺዎች ዓመታት ተስፋን የሚፈጽም እውነተኛ ተስፋ እግዚአብሔርን ይዘን ተስፋ እንዳንቆርጥ እንጠንቀቅ።ተስፋችን ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ" ይሁን እንጂ የእኛ አይሁን።ከቅዱሳን ነቢያቱ ጋር በአንድ መንፈስ ተሠርተን ልደቱን ለማየት ያብቃን።
#ጾመ ነቢያት ተስፋ ፤ #የጌታ ልደት የተስፋቸው ፍጻሜ ነውና!!!

#መልካም ጾመ ነቢያት

#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 15/2017 ዓ.ም