ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
“#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
=>ነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ "፤ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፤" መዝ 86÷1
"፤ ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል።"
(መዝሙረ ዳዊት 87: 2)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር
>>>
+ከነገደ #ይሁዳ የሚወለድ #ቅዱስ_ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ #ሌዊ (#አሮን) የተወለደች #ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች “ልጅ የላችሁም” በሚል ይናቁ ነበር::
+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን “ኅጡአ በረከት-ከጸጋ #እግዚአብሔር የራቀ” ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት #የአብርሃምና_ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::
+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች #ቅድስት_ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: “እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?” ብላ አዘነች::
+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- #ነጭ_ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::
+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::
+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) #መልአከ_ብሥራት_ቅዱስ_ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: “ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ” ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::
+እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው #እመ_ብርሃን ተጸነሰች::
“#ኦ_ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ
¤ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም” እንዳለ ሊቁ:: (#ቅዳሴ_ማርያም)
+”+ #ቅዱስ_ዼጥሮስ_ሊቀ_ሐዋርያት +”+
=>ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ዼጥሮስ መታሰቢያ ናት:: #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ #ቂሣርያ_ፊልዾስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በርስ ይከራከሩ ገቡ::
+የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን (ገና ምሥጢርን ያልተረዱ) ነበሩና አንዱ ተነስቶ “ኤልያስ ነው”: ሌላኛው “ሙሴ”: 3ኛው “ኤርምያስ ነው” በሚል ተከራከሩ:: #ቅዱስ_ዼጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው “ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ላንተስ ማን ይመስልሃል?” አሉት::
+አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: “እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን “እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው” አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ::
+ቸር አምላክ “ለምን ተጠራጠራችሁኝ” ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: “የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?” አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ::
+ጌታችን “እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?” ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዼጥሮስ ተነስቶ “#አንተ_ውእቱ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ሕያው-
አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ” አለው:: (ማቴ. 16:16)
+ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን “አንተ ዓለት (መሠረት) ነህ” ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ዼጥሮስም “#መራሑተ_መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ (ሥልጣን)” ተሰጠው::
+ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን “#አምላክ_ወልደ_አምላክ:_ወልደ_ማርያም:_አካላዊ_ቃል:_ሥግው_ቃል:_ገባሬ_ኩሉ:_የሁሉ_ፈጣሪ” ብለው ካላመኑ እንኩዋን ጽድቅ ክርስትናም የለም::
+”+ #አፄ_ናዖድ_ጻድቅ +”+
=>ሃገራችን #ኢትዮዽያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል::
+ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት (ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .)
የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን #መልክዐ_ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው::
+የጻድቁ ንጉሥ ሚስት (#ማርያም_ክብራ): ልጆቻቸው (#አፄ_ልብነ_ድንግልና #ቡርክት_ሮማነ_ወርቅ) እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ #አፄ_ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ #ድንግል_ማርያምን “እመቤቴ 8ኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?” አሏት::
+እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው “#እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ” አሏት:: በዚህ ምክንያት የ8ኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል::
=>ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ዼጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::
=>ነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
=>+”+ መሠረቶቿ "፤ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፤" መዝ 86÷1
"፤ ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ፥ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወድዳቸዋል።"
(መዝሙረ ዳዊት 87: 2)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር
>>>
✍ ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡
☞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
.
☞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
.
☞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል።
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
.
☞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
.
☞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል።
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
.
☞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል።
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
.
☞ እሁድ- #ዳግም_ትንሳኤ ይባላል።
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
☞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
.
☞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
.
☞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል።
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
.
☞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
.
☞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል።
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
.
☞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል።
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
.
☞ እሁድ- #ዳግም_ትንሳኤ ይባላል።
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
✍ ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡
☞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
.
☞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
.
☞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል።
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
.
☞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
.
☞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል።
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
.
☞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል።
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
.
☞ እሁድ- #ዳግም_ትንሳኤ ይባላል።
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
☞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
.
☞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
.
☞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል።
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
.
☞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
.
☞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል።
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
.
☞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል።
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
.
☞ እሁድ- #ዳግም_ትንሳኤ ይባላል።
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
Audio
ዓውደ ስብከት
አስተማሪ: #ልዑል_እግዚአብሔር
ተናጋሪ: #መምህር #ኢዮብ_ክንፈ
ርዕስ: #ቅድስት_ትንሳኤ
ክፍል አንድ
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
አስተማሪ: #ልዑል_እግዚአብሔር
ተናጋሪ: #መምህር #ኢዮብ_ክንፈ
ርዕስ: #ቅድስት_ትንሳኤ
ክፍል አንድ
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
Audio
ዓውደ ስብከት
አስተማሪ: #ልዑል_እግዚአብሔር
ተናጋሪ: #መምህር #ኢዮብ_ክንፈ
ርዕስ: #ቅድስት_ትንሳኤ
ክፍል ሁለት
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
አስተማሪ: #ልዑል_እግዚአብሔር
ተናጋሪ: #መምህር #ኢዮብ_ክንፈ
ርዕስ: #ቅድስት_ትንሳኤ
ክፍል ሁለት
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@Abenma
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን በዐድዋ
_____________________________
ጦርነት አስከፊ ነው የጦርነት ደግ የለውም ሆኖም በዓለማችን ላይ ቅዱስ ጦርነት ፤የመስቀል ጦርነት ተብለው የተጠሩ የጦርነት ዐይነቶች ነበሩ።
በአለፉት ሺህ ዓመታት በጥንታዊ ሀገራችን ኢትዮጲያ ከተፈጸሙ ታሪካዊ ነገሮች አንዱ በሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊ ተራዳኢነት ጀግኖች አባቶቻችን በፋሽሽት ኢጣልያ ላይ የካቲት ፳ ፫ ቀን ፲ ፰ ፻ ፹ ፰ ዓ.ም የተቀዳጁት የዐድዋ ድል ነው ይህ ድል የመላው አፍሪካ ጥቁር ሕዝቦች ድልና የነፃነት ብርሃን በመባል ይታወቃል።
#ጀግኖች_አባቶቻችንን በአድዋው ጦርነት የረዳቸው የሰማዕታት አለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕገ ወንጌልን በማስተማርና አምልኮተ ጣኦትን በመንቀፍ ስለ ፈጣሪያችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕሪ አምላክነት እየመሠከረ ከግፈኖች አረማውያን ብዙ መከራ ተቀብሎ በአደባባይ መራራ ሞትን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ሰባት ዓመታትን ከተጋደለ በኃላ ሚያዝያ ፳ ፫ ቀን የሰማዕትነትን አክሊል ተቀብሏል።
ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሚያዝያ ፳ ፫ ቀን ሰማዕትነትን ጊዮርጊስ በተቀበለበት ዕለት ከፈጣሪው ከኢየሱስ ክርስቶስ ልዮ ልዮ የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብሏል።ከተቀበለው ቃል ኪዳን መካከል በስምህ ተማጽኖ መታሰቢያህን የሚደርገውን እኔ በመከራው ቀን እረዳዋለሁ የሚል ይገኝበታል።
#ሊቀ_ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማዕትነትን አክሊለ ክብር ከተቀበለ በኃላ በአካለ ነፍስ ሆኖ ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተማኅጽኖ አቀረበ ይኸውም " ምስለ ፍልሠትኪ ደምርኒ እሙ" የፈጣሪየ የኢየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ ሰማዕትነትን ከተቀበልኩባት ከፋርስ ምድር የአጽሜ ፍልሠት ቀን ከአንቺ የፍልሰትሽ በዓል ቀን ጋር ነሐሴ ፲ ፮ ቀን ተባብሮ እንዲከበርልኝ ፈቃድሽ ይሆን በማለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመነ።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም እንዳልከው ይሆንልሃል ስለሆነም አንተም ከእግዚአብሔር አስራት ሁና የተሰጠችኝን ኢትዮጵያን ገበዝ (ጠባቂዋ) ሆነህ ጠብቃት አለችሁ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም አንቺ እንዳልሽ ይሁን እመቤቴ አለ ስለዚህም ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ገበዝ ወይም ጠባቂ ሁኖ ከእግዚአብሔር ተሹሟል።
#የቅዱስ_ጊዮርጊስ ፍልሰተ አጽም ከፋርስ ወደ ልዳ በነሐሴ ፲ ፮ ቀን ማለትም የእመቤታችን ቅዱስ ሥጋ ከጌቴ ሰማኒ ወደ መንግሥት ሰማያት በፈለሰበት (በዕርገቷ) ዕለት ተፈጽሞለታል። ይህን የቅዱስ ጊዮርጊስና የእመቤታችን ስምምነት በሚገባ የምታውቀው ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወራሪ ጠላት እና ከክፉ ነገር ሁሉ እንደሚጠብቃት ዘወትር ታምናለች።
በመሆኑም በጥንት ኢትዮጵያ የሚታወቅና ይደረግ የተበረ አንድ ነገር አለ ከቅድመ አያቶቻችን ጀምሮ የሚደረገውም ወጣት ኢትዮጵያዊን የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ማኅበርተኞች በመሆን በአንድነት ይሰበሰባሉ፤ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም በየጊዜው እየተሰበሰቡም ሰለ ፈረስ ግልቢያ ፣ስለ ጦር ጉግስ፣ የጦር ስልትና ወታደራዊ የጀግንነት ትምህርት እየተማሩ እንዲያድጉ ያደርጉ ነበር።
#አባቶቻችን በዚህ ዕድገታቸው የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስና የለገራቸው ኢትዮጵያ ፍቅር አብሮ ያድጋል የጀግንነት ወኔአቸውና ሥነ ምግባራቸውም የላቀ ይሆናል እንዲህ ሁነው የሚድጉት ኢትዮጵያዊያን በማናቸውም ነገር በቀላሉ የማይበገሩ ስለሆኑና የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት ስለማይለያቸው በየትኛውም የጦርነት ታሪክ የተሸነፉበት ጊዜ የለም።
እንደሚታወቀው በኢትዮጵያ ታሪክ አፄ አምደ ጽዮን የጦር ሰው ነበሩ።በቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ያላቸው እምነትና ተማጽኖ በእጅጉ የላቀ እንደነበርም ይነገርላቸዋል። በኢትዮጵያ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቤተ ክርስቲያን መሥራት የተስፋፋውም በእርሳቸው ዘመን ነው።
#በኢትዮጵያ የሥልጣኔ ታሪክ ዘመናዊ አስተዳደር እንዲስፋፋ ከፍተኛ ጥረት ያደረጉት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እንደ ቀድሞዎ አባቶቻችን ከኢትዮጵያ ገበዝ(ጠባቂ) ከሰማዕት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የነበራቸው ፍቅር እጅግ የላቀ ነበር ። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የነገሱበት ዘመን በጊዜው የነበሩ የኢጣልያ ባለ ሥልጣኖች ቃላቸውን እየለወጡና እያታለሉ ሀገራችን ኢትዮጵያ በቀኝ ግዛት ለመያዝ ቆርጠው የተነሱበት ዘመን ነበር።
የኢጣልያን ጦር መረብን ተሻግሮ ወደ ትግራይ እየገሰገሰ መምጣቱ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በሰሙ ጊዜ በ ፲ ፰ ፻ ፹ ፰ ዓ.ም የክተት አዋጅ አድርገው በጥቅምት ወር ወደ ትግራይ ሄዱ ጣሊያንን ለመፋለም ወደ ትግራይ ሲሄዱ ሁል ጊዜ ኢትዮጵያን በመርዳት የሚታወቀውን የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስንእና የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ታቦት ይዘው ነበር የሄዱት ወቅቱም የዐቢይ ጾም መጀመሪ ስለነበር አብሯቸው የዘመተው አብዛኛው አርሶ አደር ገበሬ ጾሙን ሳይታ እየጾመ ነበር የተከተላቸው። እርሳቸውም ቢሆኑ ምንም እንኳ ዕለቱ እሁድ ቢሆንም ቅዳሴ ገብተው እስከ ረፋዱ ሦስት ሰዓት አስቀድሰው ነው ወደ ጦርነቱ የገቡት ።
..............ቀጣዮን የመጨረሻ ክፍል ይመልከቱ........
#ዐውደ_ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/112544300256976/posts/277932900384781/?app=fbl
_____________________________
ጦርነት አስከፊ ነው የጦርነት ደግ የለውም ሆኖም በዓለማችን ላይ ቅዱስ ጦርነት ፤የመስቀል ጦርነት ተብለው የተጠሩ የጦርነት ዐይነቶች ነበሩ።
በአለፉት ሺህ ዓመታት በጥንታዊ ሀገራችን ኢትዮጲያ ከተፈጸሙ ታሪካዊ ነገሮች አንዱ በሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊ ተራዳኢነት ጀግኖች አባቶቻችን በፋሽሽት ኢጣልያ ላይ የካቲት ፳ ፫ ቀን ፲ ፰ ፻ ፹ ፰ ዓ.ም የተቀዳጁት የዐድዋ ድል ነው ይህ ድል የመላው አፍሪካ ጥቁር ሕዝቦች ድልና የነፃነት ብርሃን በመባል ይታወቃል።
#ጀግኖች_አባቶቻችንን በአድዋው ጦርነት የረዳቸው የሰማዕታት አለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕገ ወንጌልን በማስተማርና አምልኮተ ጣኦትን በመንቀፍ ስለ ፈጣሪያችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕሪ አምላክነት እየመሠከረ ከግፈኖች አረማውያን ብዙ መከራ ተቀብሎ በአደባባይ መራራ ሞትን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ሰባት ዓመታትን ከተጋደለ በኃላ ሚያዝያ ፳ ፫ ቀን የሰማዕትነትን አክሊል ተቀብሏል።
ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሚያዝያ ፳ ፫ ቀን ሰማዕትነትን ጊዮርጊስ በተቀበለበት ዕለት ከፈጣሪው ከኢየሱስ ክርስቶስ ልዮ ልዮ የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብሏል።ከተቀበለው ቃል ኪዳን መካከል በስምህ ተማጽኖ መታሰቢያህን የሚደርገውን እኔ በመከራው ቀን እረዳዋለሁ የሚል ይገኝበታል።
#ሊቀ_ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማዕትነትን አክሊለ ክብር ከተቀበለ በኃላ በአካለ ነፍስ ሆኖ ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተማኅጽኖ አቀረበ ይኸውም " ምስለ ፍልሠትኪ ደምርኒ እሙ" የፈጣሪየ የኢየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ ሰማዕትነትን ከተቀበልኩባት ከፋርስ ምድር የአጽሜ ፍልሠት ቀን ከአንቺ የፍልሰትሽ በዓል ቀን ጋር ነሐሴ ፲ ፮ ቀን ተባብሮ እንዲከበርልኝ ፈቃድሽ ይሆን በማለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመነ።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም እንዳልከው ይሆንልሃል ስለሆነም አንተም ከእግዚአብሔር አስራት ሁና የተሰጠችኝን ኢትዮጵያን ገበዝ (ጠባቂዋ) ሆነህ ጠብቃት አለችሁ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም አንቺ እንዳልሽ ይሁን እመቤቴ አለ ስለዚህም ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ገበዝ ወይም ጠባቂ ሁኖ ከእግዚአብሔር ተሹሟል።
#የቅዱስ_ጊዮርጊስ ፍልሰተ አጽም ከፋርስ ወደ ልዳ በነሐሴ ፲ ፮ ቀን ማለትም የእመቤታችን ቅዱስ ሥጋ ከጌቴ ሰማኒ ወደ መንግሥት ሰማያት በፈለሰበት (በዕርገቷ) ዕለት ተፈጽሞለታል። ይህን የቅዱስ ጊዮርጊስና የእመቤታችን ስምምነት በሚገባ የምታውቀው ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወራሪ ጠላት እና ከክፉ ነገር ሁሉ እንደሚጠብቃት ዘወትር ታምናለች።
በመሆኑም በጥንት ኢትዮጵያ የሚታወቅና ይደረግ የተበረ አንድ ነገር አለ ከቅድመ አያቶቻችን ጀምሮ የሚደረገውም ወጣት ኢትዮጵያዊን የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ማኅበርተኞች በመሆን በአንድነት ይሰበሰባሉ፤ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም በየጊዜው እየተሰበሰቡም ሰለ ፈረስ ግልቢያ ፣ስለ ጦር ጉግስ፣ የጦር ስልትና ወታደራዊ የጀግንነት ትምህርት እየተማሩ እንዲያድጉ ያደርጉ ነበር።
#አባቶቻችን በዚህ ዕድገታቸው የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስና የለገራቸው ኢትዮጵያ ፍቅር አብሮ ያድጋል የጀግንነት ወኔአቸውና ሥነ ምግባራቸውም የላቀ ይሆናል እንዲህ ሁነው የሚድጉት ኢትዮጵያዊያን በማናቸውም ነገር በቀላሉ የማይበገሩ ስለሆኑና የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት ስለማይለያቸው በየትኛውም የጦርነት ታሪክ የተሸነፉበት ጊዜ የለም።
እንደሚታወቀው በኢትዮጵያ ታሪክ አፄ አምደ ጽዮን የጦር ሰው ነበሩ።በቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ያላቸው እምነትና ተማጽኖ በእጅጉ የላቀ እንደነበርም ይነገርላቸዋል። በኢትዮጵያ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቤተ ክርስቲያን መሥራት የተስፋፋውም በእርሳቸው ዘመን ነው።
#በኢትዮጵያ የሥልጣኔ ታሪክ ዘመናዊ አስተዳደር እንዲስፋፋ ከፍተኛ ጥረት ያደረጉት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እንደ ቀድሞዎ አባቶቻችን ከኢትዮጵያ ገበዝ(ጠባቂ) ከሰማዕት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የነበራቸው ፍቅር እጅግ የላቀ ነበር ። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የነገሱበት ዘመን በጊዜው የነበሩ የኢጣልያ ባለ ሥልጣኖች ቃላቸውን እየለወጡና እያታለሉ ሀገራችን ኢትዮጵያ በቀኝ ግዛት ለመያዝ ቆርጠው የተነሱበት ዘመን ነበር።
የኢጣልያን ጦር መረብን ተሻግሮ ወደ ትግራይ እየገሰገሰ መምጣቱ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በሰሙ ጊዜ በ ፲ ፰ ፻ ፹ ፰ ዓ.ም የክተት አዋጅ አድርገው በጥቅምት ወር ወደ ትግራይ ሄዱ ጣሊያንን ለመፋለም ወደ ትግራይ ሲሄዱ ሁል ጊዜ ኢትዮጵያን በመርዳት የሚታወቀውን የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስንእና የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ታቦት ይዘው ነበር የሄዱት ወቅቱም የዐቢይ ጾም መጀመሪ ስለነበር አብሯቸው የዘመተው አብዛኛው አርሶ አደር ገበሬ ጾሙን ሳይታ እየጾመ ነበር የተከተላቸው። እርሳቸውም ቢሆኑ ምንም እንኳ ዕለቱ እሁድ ቢሆንም ቅዳሴ ገብተው እስከ ረፋዱ ሦስት ሰዓት አስቀድሰው ነው ወደ ጦርነቱ የገቡት ።
..............ቀጣዮን የመጨረሻ ክፍል ይመልከቱ........
#ዐውደ_ምሕረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/112544300256976/posts/277932900384781/?app=fbl
#ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን በዐድዋ
____________________________
...የመጨረሻውና አስደማሚው ኩነት...
#ዳግማዊ_አፄ ምኒልክ ታቦተ ጊዮርጊስ በድንኳን ይዘው አድዋ ላይ ሰፍረው በነበረ ጊዜ ባንዳ የነበረ ሰው በኢትዮጵያ የጦር ሰፈር መሰላቸት እንዳለና ስንቅ እያለቀ መሆኑን ለኢጣሊያኖት እየሄደ ያወራ ነበር። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ይህን ወሬ በሰሙ ጊዜ በድንኳኑ ውስጥ የቅዱስ የጊዮርጊስ ታቦት የሚገለግለውን ካህን ጠርተው እንደ አባቶቼ ተዋግቼ እንድሞት እባክህን ጦርነቱን አስጀምረው ብለህ ንገርልኝ ሲሉ ይልኩታል።እርሱም እንደታዘዘው ያደርጋል።
ጦርነቱ ሲጀመር የኢትዮጲያ ወታደሮች በኢጣልያን ጦር ይጠቁ ጀመር ለዚህም ትልቁ ምክንያት ጀግንነታቸው ነበር ጣሊያኖች ምሽግ ይዘው ሲተኩሱ ጀግኖች አባቶቻችን ግን ምሽግ ውስጥ ተደብቆ መተኮስን እና ማጥቃትን እንደ ነውር በመቁጠር ደረታቸውን እየገለበጡ ፊት ለፊት ይዋጉ ስለነበር ነው ።በእውነቱ ይህ.ግሩም ድንቅ የሆነ ጀግንነት ነው!...
#እቴጌ_ጣይቱም ኢጣሊያ ይጠጣው የነበረውን የውኃ ጉድጓድ አስያዙት በዚህም ጣልያን ትንሽ ተዳከመ ሆኖም ሐበሻ መጠቃቱን አልቀረም ነበር ። ይህን የሐበሻን መጠቃት የተመለከተው የልዳው ሰማዕት ከእመቤታችን ጋር የገባውን ቃል ይፈጽም ዘንድ በነጭ አባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ መጥቶ ኢጣልያኖችን ፈጃቸው ድሉም የኢትዮጵያ ሆነ። ይህንንም በምርኮ የተያዙ የኢጣሊያ ጭፍሮች በአድናቆት ሆነው መስክረዋል።
በዚህም የድል ወቅት በጎጃም ዲማ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በፍሬም የተሰቀለ ትልቅ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ነበር:: ጠዋት የገዳሙ እማሆይ አቃቢ ግብረ ማህረዕ ለመፈጸም ይህን ሥዕል ሊሳለሙ ሲገቡ ሥዕሉን ከቦታው ያጡታል በኃላ ወደ ማታ ይህው ሥዕል እየበረረ መጥቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባ ያዩታል እማሆይም አቃቢም አባቴ ጊዮርጊስ የት ውለህ መምጣትህ ነው ? ቢሉት ጌታሽን " ምኒልክን ስረዳው ውዬ መምጣቴ ነው" ብሎ በስብአዊ ልሣን አናገራቸው።
#እማ_ሆይም ከሥዕሉ በጦርነቱ የኢትዮያን አሸናፊነት ተረድተው በዕልልታ አቀለጡት:: አፄ ምኒልክም ከድሉ ሲመለሱ ከደስታቸው የተነሳ በአዲስ አበባ ለሰማዕቱ ውለታ ይሆን ዘንድ ፒያሳ የሚገኘውን የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ሰሩለት::
ዋቢ:- ልሳነ ተዋህዶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ጥር ፪ ሺህ ፫ ዓ.ም ያሳተመው መጽሔት
................ይቆየን ...........
#የእግዚአብሔር_ቸርነት_የድንግል_ማርያም_አማላጅነት_የሰማዕቱ_የቅዱስ_ጊዮርጊስ_ጥበቃና_ረድኤት አይለየን!
" ዐውደ ምሕረት የእናንተ "
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/112544300256976/posts/277932900384781/?app=fbl
____________________________
...የመጨረሻውና አስደማሚው ኩነት...
#ዳግማዊ_አፄ ምኒልክ ታቦተ ጊዮርጊስ በድንኳን ይዘው አድዋ ላይ ሰፍረው በነበረ ጊዜ ባንዳ የነበረ ሰው በኢትዮጵያ የጦር ሰፈር መሰላቸት እንዳለና ስንቅ እያለቀ መሆኑን ለኢጣሊያኖት እየሄደ ያወራ ነበር። ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ይህን ወሬ በሰሙ ጊዜ በድንኳኑ ውስጥ የቅዱስ የጊዮርጊስ ታቦት የሚገለግለውን ካህን ጠርተው እንደ አባቶቼ ተዋግቼ እንድሞት እባክህን ጦርነቱን አስጀምረው ብለህ ንገርልኝ ሲሉ ይልኩታል።እርሱም እንደታዘዘው ያደርጋል።
ጦርነቱ ሲጀመር የኢትዮጲያ ወታደሮች በኢጣልያን ጦር ይጠቁ ጀመር ለዚህም ትልቁ ምክንያት ጀግንነታቸው ነበር ጣሊያኖች ምሽግ ይዘው ሲተኩሱ ጀግኖች አባቶቻችን ግን ምሽግ ውስጥ ተደብቆ መተኮስን እና ማጥቃትን እንደ ነውር በመቁጠር ደረታቸውን እየገለበጡ ፊት ለፊት ይዋጉ ስለነበር ነው ።በእውነቱ ይህ.ግሩም ድንቅ የሆነ ጀግንነት ነው!...
#እቴጌ_ጣይቱም ኢጣሊያ ይጠጣው የነበረውን የውኃ ጉድጓድ አስያዙት በዚህም ጣልያን ትንሽ ተዳከመ ሆኖም ሐበሻ መጠቃቱን አልቀረም ነበር ። ይህን የሐበሻን መጠቃት የተመለከተው የልዳው ሰማዕት ከእመቤታችን ጋር የገባውን ቃል ይፈጽም ዘንድ በነጭ አባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ መጥቶ ኢጣልያኖችን ፈጃቸው ድሉም የኢትዮጵያ ሆነ። ይህንንም በምርኮ የተያዙ የኢጣሊያ ጭፍሮች በአድናቆት ሆነው መስክረዋል።
በዚህም የድል ወቅት በጎጃም ዲማ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በፍሬም የተሰቀለ ትልቅ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ነበር:: ጠዋት የገዳሙ እማሆይ አቃቢ ግብረ ማህረዕ ለመፈጸም ይህን ሥዕል ሊሳለሙ ሲገቡ ሥዕሉን ከቦታው ያጡታል በኃላ ወደ ማታ ይህው ሥዕል እየበረረ መጥቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባ ያዩታል እማሆይም አቃቢም አባቴ ጊዮርጊስ የት ውለህ መምጣትህ ነው ? ቢሉት ጌታሽን " ምኒልክን ስረዳው ውዬ መምጣቴ ነው" ብሎ በስብአዊ ልሣን አናገራቸው።
#እማ_ሆይም ከሥዕሉ በጦርነቱ የኢትዮያን አሸናፊነት ተረድተው በዕልልታ አቀለጡት:: አፄ ምኒልክም ከድሉ ሲመለሱ ከደስታቸው የተነሳ በአዲስ አበባ ለሰማዕቱ ውለታ ይሆን ዘንድ ፒያሳ የሚገኘውን የገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን ሰሩለት::
ዋቢ:- ልሳነ ተዋህዶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ጥር ፪ ሺህ ፫ ዓ.ም ያሳተመው መጽሔት
................ይቆየን ...........
#የእግዚአብሔር_ቸርነት_የድንግል_ማርያም_አማላጅነት_የሰማዕቱ_የቅዱስ_ጊዮርጊስ_ጥበቃና_ረድኤት አይለየን!
" ዐውደ ምሕረት የእናንተ "
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/112544300256976/posts/277932900384781/?app=fbl
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
#ዛቲ_ዕለት_ቅድስት_ይዕቲ
(ይህቺ ቀን የተቀደሰች ናት)
*****************************
#ቅድስት_ማለት የተለየች የጸናች ክብርት ማለት ነው:: ቤተ ክርስቲያንም በዚህ በዐብይ ጾም ሁለተኛውን ሳምንት ቅድስ ብላ በመሰየም የሰንበትን ቅድስና ታስባለች ::
ሰንበትን ቅድስት ያሰኛት ምንድነው?
_________________________
ፈጣሪ ዓለማት ልዑል እግዚአብሔር በሰድስቱ ዕለታት ፍጥረታትን ከፈጠረ በኃላ በሰባተኛው ዕለት ከሰራው ሥራ ሁሉ አረፈ "ለሙሴም የሰንበትን ቀን ትቀድሳት ዘንድ አሰብ "የምትለውን ትዕዛዝ ሰጠ ስለዚህ ሰንበትን ቅድስት ያሰኛት ከስራ ሁሉ የሚታረፍባት ሕመምተኛ የሚጠየቅባት ወደ ቤተ እግዚአብሔር የሚገሰገስባት ቀን በመሆኗ ነው ::
በግብራቸው የተነሳ ዕረፍት እየተባሉ የሚጠሩ
***********************************
1) (ሰንበት ክርስቲያን )ዕለት እሁድ :- ዕረፍት ተብላ ትጠራለች: ዕለተ እሁድ በሌላ ስሟ ሰንበተ ክርስቲያንም ተብላ ትጠራለች :: አንዳንድ ጊዜ ሰንበት እሁድ ከሆነች ቅዳሜ ታድያ ምንድነች??? ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል :: አስቀድሞ ዕለተ ቅዳሜ የአይሁድ ሰንበት ነበረች ጌታችንም እንደተናገረው ሕግ ና ነቢያትን ልፈጽም እንጂ ልሽራቸው አልመጣውም እንዳለ የአይሁድ ሰንበት ቅዳሜም አልተሻረችም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ቀዳዊት ሰንበት የቀደመች ሰንበት ብላ ታስባታለችች :: ማቴ5÷17 አንድም ደግሞ የኦሪት ሥርዓቶች ሁሉ ለአዲስ ኪዳን ሥርዓቶች ምሳሌ ጥላ መርገፍ ናቸውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ቅዳሜን እንደ ምሳሌ አድርጋ እሁድን አማናዊት ሰንበት አድርጋ ታስባቸዋለች ::
ዕለተ እሁድ( ሰንበተ ክርስቲያን)
*ጥንተ ዕለት ናት :- ፍጥረታት መፈጠር የጀመሩባት ዕለት ናትና "ይህቺ ዕለት ከ7ቱ ዕለታት ቀድማ የተገኘች ናት እንጂ በኃላ የተገኘች አይደለችም " እንዳለ ቅዱስ አትናቲዮስ በኩረ በዓላት ናት :-
* #የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ናትና ዓለም የተገኘባት
* #ወልድ ሰው የሆነባት
* # ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳባት
* #ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣበት ዕለት ጭምር ናት::
2) #እመቤታችን ዕረፍት ተብላ ትጠራለች
____________________________
ከ5500 ዘመን የድካም የመከራ ጊዜ ሁሉ በእርሷ እረፍትን አግኝተናልና :: እንዴት ቢሉ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ባበሰራት ጊዜ ለዓለም መዳን ምክንያት ትሆኚ ዘንድ መርጦሻል ብሎ ፍቃዷን በጠየቀ ጊዜ "ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ "እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" በማለት ለድኅነተ ዓለም ምክንያት እረፍት ሆናለች:: #ሉቃ 1÷26
3) #ቅዱሳን :- እረፍት ተብለው ይጠራሉ::ቅዱሳን በሳኦል መንፈስ ለተያዘችው ደካማዋ ዓለም እረፍት ናቸው " እንዲህም ሆነ፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ ክፉ መንፈስ በሳኦል ላይ በሆነ ጊዜ ዳዊት በገና ይዞ በእጁ ይመታ ነበር፤ ሳኦልንም ደስ ያሰኘው ያሳርፈውም ነበር፥ ክፉ መንፈስም ከእርሱ ይርቅ ነበር። (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 16÷23) አንድም ጻድቃን በጸሎታቸው ሕዝብ የሚያሳርፉሁ ናቸው ጻድቃንም በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋልና በመወለዳቸውም ብዙዎች ደስ ተሰኝተዋልና ምሳ 29÷2 ሉቃ 1÷14 ያዕ 5÷16
4) #ቅድስት_ቤተ ክርስቲያን እረፍት ትባላለች :-
__________________________________
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እግዚአብሔር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝም የለም በለመለመ መስክ ያሰማራኛል በእረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል " ብሎ ቤተ እግዚአብሔርን እንደ እረፍት ሥፍራ በውስጧ የሚፈሰውን ቃለ እግዚአብሔርን ደግሞ እንደ መብል እንደ መጠጥ አድርጎ ተናግሯል:: መዝ 22(23)÷1 አንድም የእረፍት ቦታ የሆነችው የመንግስተ ሰማያት የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ናትና ዕረፍት ተብላ ትጠራለች ::
5) #መንግሥተ ሰማያት ራሷ እረፍት ትባላለች
_______________________________
እስራኤል ዘሥጋ ድካም ከበዛባት ከምድረ ግብጽ ወተው እረፍት የሆነችውን ምድረ ከንዓንን ወረሰዋል እኛም እስራኤል ዘነፍሶች ከዚህች ድካም ከበዛባት ዓለም እረፍት የምናገኘው በመንግስተ ሰማያት ነውና መንግስተ ሰማያት እረፍት ትባላለች :: " ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 2:9)
6) #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ዕረፍት ይባላል :-
___________________________________
" እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።" ብሏልና ዕረፍታችን ነው (የማቴዎስ ወንጌል 11:28) አንድም የእግዚአብሔር መንግስት(የዕረፍት ሥፍራ) ከወድየት አለች ብለው በጠየቁት ጊዜ " ደግሞም። እንኋት በዚህ ወይም። እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።" (የሉቃስ ወንጌል 17:21) ይህን ያለው በመካከላቸው የነበረው እርሱ መንግስተ ሰማያት የእረፍት ሥፍራ ወይም እረፍታችን በመሆኑ ነው ::
ስለዚህ እኛ ክርስቲያኖች የሰንበትን ቅድስና ስናስብ እግዚአብሔርን እመቤታችንን ቅዱሳንን መንግስተ ሰማያትን ሁሉ ታሳቢ ማድረግ ይገባናል ማለት ነው::
#የግርጌ_ማስታወሻ
++++++++++++++
እረፍትን ለማግኘት አስቀድሞ ሥራ ሊኖር ይገባል ሥራ በሌለበት እረፍት የለም:: እንድ ሰው አረፈ ለማለት አስቀድሞ ሥራ ሰራ ሊባል ይገባዋል:: እግዚአብሔርም ከሰራው ሥራ ሁለ አረፈ ተብሎ ተጻፈ እንጂ አረፈ ተብሎ ብቻ አልተጻፈልንም በመሆኑም እኛ ክርስቲያኖች እረፍተ መንግስተ ሰማያትን እረፍት እግዚአብሔርን እረፍት እመቤታችንን እረፍት ቅዱሳንን ለማግኘት በጎ ሥራን ሁሉ ልንሰራ ያስፈልጋል :: አንድ ሊቅ በሰንበት አንድ ሥራ ሲሰሩ የኔ ቢጤ ጨዋ መቶ ምነው አባ እግዚአብሔር እንኳን ባረፈበት ቀን በሰንበት ለምን ሥራ ይሰራሉ አላቸው ሊቁም ፈገግ ብለው አዮትና ልጄ እርሱ ኮ ያረፈው ሥራውን ሁሉ ጨርሶ ነው እኔ ምን ሰርቼ ነው የማርፈው አሉት ይባላል :: በሰንበት ለሰንበት የሚገባ ሥራ ልንሰራበት ይገባል እንጂ ሥራ ፈተን መቀመጥ አይገባንም ሥራ የፈታ አህምሮ የሰይጣን ቢሮ ነውና ያለ ሥራ የተቀመጠ ሰው ሊስት ሊሳሳት ይችላል::
በሰንበት ዝም ብሎ ከመቀመጥ ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሄድ የታመመ ካለ መጠየቅ መጸለይ ሌላም ሌላም የትሩፋት ሥራ ልንሰራ ይገባል :: ይህን ካደረግን ቅድስት ከሆነችው ከሰንበት ረድኤትና በረከትን እናገኛለን::
.........ይቆየን...........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ /ማርያም
የካቲት 12/2010 ዓም
(ይህቺ ቀን የተቀደሰች ናት)
*****************************
#ቅድስት_ማለት የተለየች የጸናች ክብርት ማለት ነው:: ቤተ ክርስቲያንም በዚህ በዐብይ ጾም ሁለተኛውን ሳምንት ቅድስ ብላ በመሰየም የሰንበትን ቅድስና ታስባለች ::
ሰንበትን ቅድስት ያሰኛት ምንድነው?
_________________________
ፈጣሪ ዓለማት ልዑል እግዚአብሔር በሰድስቱ ዕለታት ፍጥረታትን ከፈጠረ በኃላ በሰባተኛው ዕለት ከሰራው ሥራ ሁሉ አረፈ "ለሙሴም የሰንበትን ቀን ትቀድሳት ዘንድ አሰብ "የምትለውን ትዕዛዝ ሰጠ ስለዚህ ሰንበትን ቅድስት ያሰኛት ከስራ ሁሉ የሚታረፍባት ሕመምተኛ የሚጠየቅባት ወደ ቤተ እግዚአብሔር የሚገሰገስባት ቀን በመሆኗ ነው ::
በግብራቸው የተነሳ ዕረፍት እየተባሉ የሚጠሩ
***********************************
1) (ሰንበት ክርስቲያን )ዕለት እሁድ :- ዕረፍት ተብላ ትጠራለች: ዕለተ እሁድ በሌላ ስሟ ሰንበተ ክርስቲያንም ተብላ ትጠራለች :: አንዳንድ ጊዜ ሰንበት እሁድ ከሆነች ቅዳሜ ታድያ ምንድነች??? ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል :: አስቀድሞ ዕለተ ቅዳሜ የአይሁድ ሰንበት ነበረች ጌታችንም እንደተናገረው ሕግ ና ነቢያትን ልፈጽም እንጂ ልሽራቸው አልመጣውም እንዳለ የአይሁድ ሰንበት ቅዳሜም አልተሻረችም ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ቀዳዊት ሰንበት የቀደመች ሰንበት ብላ ታስባታለችች :: ማቴ5÷17 አንድም ደግሞ የኦሪት ሥርዓቶች ሁሉ ለአዲስ ኪዳን ሥርዓቶች ምሳሌ ጥላ መርገፍ ናቸውና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ቅዳሜን እንደ ምሳሌ አድርጋ እሁድን አማናዊት ሰንበት አድርጋ ታስባቸዋለች ::
ዕለተ እሁድ( ሰንበተ ክርስቲያን)
*ጥንተ ዕለት ናት :- ፍጥረታት መፈጠር የጀመሩባት ዕለት ናትና "ይህቺ ዕለት ከ7ቱ ዕለታት ቀድማ የተገኘች ናት እንጂ በኃላ የተገኘች አይደለችም " እንዳለ ቅዱስ አትናቲዮስ በኩረ በዓላት ናት :-
* #የበዓላት ሁሉ መጀመሪያ ናትና ዓለም የተገኘባት
* #ወልድ ሰው የሆነባት
* # ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳባት
* #ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣበት ዕለት ጭምር ናት::
2) #እመቤታችን ዕረፍት ተብላ ትጠራለች
____________________________
ከ5500 ዘመን የድካም የመከራ ጊዜ ሁሉ በእርሷ እረፍትን አግኝተናልና :: እንዴት ቢሉ መላእኩ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ባበሰራት ጊዜ ለዓለም መዳን ምክንያት ትሆኚ ዘንድ መርጦሻል ብሎ ፍቃዷን በጠየቀ ጊዜ "ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ "እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" በማለት ለድኅነተ ዓለም ምክንያት እረፍት ሆናለች:: #ሉቃ 1÷26
3) #ቅዱሳን :- እረፍት ተብለው ይጠራሉ::ቅዱሳን በሳኦል መንፈስ ለተያዘችው ደካማዋ ዓለም እረፍት ናቸው " እንዲህም ሆነ፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ ክፉ መንፈስ በሳኦል ላይ በሆነ ጊዜ ዳዊት በገና ይዞ በእጁ ይመታ ነበር፤ ሳኦልንም ደስ ያሰኘው ያሳርፈውም ነበር፥ ክፉ መንፈስም ከእርሱ ይርቅ ነበር። (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 16÷23) አንድም ጻድቃን በጸሎታቸው ሕዝብ የሚያሳርፉሁ ናቸው ጻድቃንም በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋልና በመወለዳቸውም ብዙዎች ደስ ተሰኝተዋልና ምሳ 29÷2 ሉቃ 1÷14 ያዕ 5÷16
4) #ቅድስት_ቤተ ክርስቲያን እረፍት ትባላለች :-
__________________________________
ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት እግዚአብሔር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝም የለም በለመለመ መስክ ያሰማራኛል በእረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል " ብሎ ቤተ እግዚአብሔርን እንደ እረፍት ሥፍራ በውስጧ የሚፈሰውን ቃለ እግዚአብሔርን ደግሞ እንደ መብል እንደ መጠጥ አድርጎ ተናግሯል:: መዝ 22(23)÷1 አንድም የእረፍት ቦታ የሆነችው የመንግስተ ሰማያት የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ናትና ዕረፍት ተብላ ትጠራለች ::
5) #መንግሥተ ሰማያት ራሷ እረፍት ትባላለች
_______________________________
እስራኤል ዘሥጋ ድካም ከበዛባት ከምድረ ግብጽ ወተው እረፍት የሆነችውን ምድረ ከንዓንን ወረሰዋል እኛም እስራኤል ዘነፍሶች ከዚህች ድካም ከበዛባት ዓለም እረፍት የምናገኘው በመንግስተ ሰማያት ነውና መንግስተ ሰማያት እረፍት ትባላለች :: " ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 2:9)
6) #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ዕረፍት ይባላል :-
___________________________________
" እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።" ብሏልና ዕረፍታችን ነው (የማቴዎስ ወንጌል 11:28) አንድም የእግዚአብሔር መንግስት(የዕረፍት ሥፍራ) ከወድየት አለች ብለው በጠየቁት ጊዜ " ደግሞም። እንኋት በዚህ ወይም። እንኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።" (የሉቃስ ወንጌል 17:21) ይህን ያለው በመካከላቸው የነበረው እርሱ መንግስተ ሰማያት የእረፍት ሥፍራ ወይም እረፍታችን በመሆኑ ነው ::
ስለዚህ እኛ ክርስቲያኖች የሰንበትን ቅድስና ስናስብ እግዚአብሔርን እመቤታችንን ቅዱሳንን መንግስተ ሰማያትን ሁሉ ታሳቢ ማድረግ ይገባናል ማለት ነው::
#የግርጌ_ማስታወሻ
++++++++++++++
እረፍትን ለማግኘት አስቀድሞ ሥራ ሊኖር ይገባል ሥራ በሌለበት እረፍት የለም:: እንድ ሰው አረፈ ለማለት አስቀድሞ ሥራ ሰራ ሊባል ይገባዋል:: እግዚአብሔርም ከሰራው ሥራ ሁለ አረፈ ተብሎ ተጻፈ እንጂ አረፈ ተብሎ ብቻ አልተጻፈልንም በመሆኑም እኛ ክርስቲያኖች እረፍተ መንግስተ ሰማያትን እረፍት እግዚአብሔርን እረፍት እመቤታችንን እረፍት ቅዱሳንን ለማግኘት በጎ ሥራን ሁሉ ልንሰራ ያስፈልጋል :: አንድ ሊቅ በሰንበት አንድ ሥራ ሲሰሩ የኔ ቢጤ ጨዋ መቶ ምነው አባ እግዚአብሔር እንኳን ባረፈበት ቀን በሰንበት ለምን ሥራ ይሰራሉ አላቸው ሊቁም ፈገግ ብለው አዮትና ልጄ እርሱ ኮ ያረፈው ሥራውን ሁሉ ጨርሶ ነው እኔ ምን ሰርቼ ነው የማርፈው አሉት ይባላል :: በሰንበት ለሰንበት የሚገባ ሥራ ልንሰራበት ይገባል እንጂ ሥራ ፈተን መቀመጥ አይገባንም ሥራ የፈታ አህምሮ የሰይጣን ቢሮ ነውና ያለ ሥራ የተቀመጠ ሰው ሊስት ሊሳሳት ይችላል::
በሰንበት ዝም ብሎ ከመቀመጥ ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሄድ የታመመ ካለ መጠየቅ መጸለይ ሌላም ሌላም የትሩፋት ሥራ ልንሰራ ይገባል :: ይህን ካደረግን ቅድስት ከሆነችው ከሰንበት ረድኤትና በረከትን እናገኛለን::
.........ይቆየን...........
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ /ማርያም
የካቲት 12/2010 ዓም
✍ ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡
.
☞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
.
☞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
.
☞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል።
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
.
☞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
.
☞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል።
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
.
☞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል።
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
.
☞ እሁድ- #ዳግም_ትንሳኤ ይባላል።
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
.
.
☞ ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል።
ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
.
☞ ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
.
☞ ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል።
በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
.
☞ ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል።
በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
.
☞ አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል።
በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
.
☞ ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል።
በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
.
☞ እሁድ- #ዳግም_ትንሳኤ ይባላል።
በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤🎤
📢 @AwediMeherit📢
📢 @AwediMeherit📢
📢📢📢📢📢📢📢📢
.
#ኑ_ይህን_ድንቅ_እዩ !
______________
#የእመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ"፭ ቀናት ያክል የመገለጥ በዓል
#ከቅዱሳን_ክብር_የማርያም_ክብር_ይበልጣል ፤ የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማሕፀንዋ ተሸከመችው። ይህች ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች ከሦስቱ አካል ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና። የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት።
#ለቅዱሳን_ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት። በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሁኗልና።
#ኑ_ይህንድንቅ_እዩ። ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፤ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፤ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት።
የማይታወቅ ተገለጠ፤ የማይታይ ታየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በርግጥ ሰው ሆነ። ትላንት የነበረው ዛሬም ያለው መቼም የሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባሕርይ ነው። #ቅድስት_ሆይ_ለምኝልን።
____ሶሪያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_የረቡዕ ውዳሴ ማርያም____
______________
#የእመቤታችን በደብረ ምጥማቅ ለ"፭ ቀናት ያክል የመገለጥ በዓል
#ከቅዱሳን_ክብር_የማርያም_ክብር_ይበልጣል ፤ የአብን ቃል ለመቀበል በተገባ ተገኝታለችና። መላእክት የሚፈሩትን ትጉሆች በሰማያት የሚያመሰግኑትን ድንግል ማርያም በማሕፀንዋ ተሸከመችው። ይህች ከኪሩቤል ትበልጣለች፤ ከሱራፌልም ትበልጣለች ከሦስቱ አካል ለአንዱ ማደሪያ ሆናለችና። የነቢያት ሀገራቸው ኢየሩሳሌም ይህች ናት።
#ለቅዱሳን_ሁሉ የደስታቸው ማደሪያ ናት። በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሁኗልና።
#ኑ_ይህንድንቅ_እዩ። ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና፤ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፤ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት።
የማይታወቅ ተገለጠ፤ የማይታይ ታየ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በርግጥ ሰው ሆነ። ትላንት የነበረው ዛሬም ያለው መቼም የሚኖረው ኢየሱስ ክርስቶስ እንሰግድለትና እናመስግነው ዘንድ አንድ ባሕርይ ነው። #ቅድስት_ሆይ_ለምኝልን።
____ሶሪያዊው_ቅዱስ_ኤፍሬም_የረቡዕ ውዳሴ ማርያም____
❤ውድ ታዳሚዎቻችን እንደምን ዋላችሁ (አደራችሁ) ...አሜን ስለ ቸርነቱ እግዚአብሔር አምላክ የተመሰገነ ይሁን አትለይምና እመ አምላክ ወላዲተ አምላክ #ቅድስት_ድንግል_ማርያምም እንደተሰጣት ከፍ ያለ ጸጋ የተመሠገነች ትሁንልን አሜን..!::
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
እነሆ ተወዳጁ የምን እንጠይቅልዎ መርኃ ግብር አሁን ጀምሯል ጥያቄዎን በሚከተሉት አድራሻዎች ይስደዱልን ሊቃውንትን ጠይቀን መጻሕፍትን አገላብጠን ቤተ ክርስቲያናዊ ምላሽ እንሰጥበታለን።
👇👇👇👇👇
@YEAWEDIMERITE
👇👇👇👇👇👇
ዓውደ ምሕረት የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ !
__________________________
#የሀገር የሌማት ትሩፋት #ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን ናት !!!
ያለ እርሷ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለም! ስለዚህ አትጨቁኟት
" የተሰወረ መና ያለብሽ #ንጹዑ_የወርቅ_መሶብ አንቺ ነሽ !
|ሶሪያዊው #ቅዱስ ኤፍሬም
__________________________
#የሀገር የሌማት ትሩፋት #ቅድስት_ቤተ_ክርስቲያን ናት !!!
ያለ እርሷ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለም! ስለዚህ አትጨቁኟት
" የተሰወረ መና ያለብሽ #ንጹዑ_የወርቅ_መሶብ አንቺ ነሽ !
|ሶሪያዊው #ቅዱስ ኤፍሬም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Eyob kinfe)
"ዕርገተ ክርስቶስ እንደ ሃይማኖት"
#በጸሎተ ሃይማኖታችን ከምንመሰክራቸው ምስክርነቶች አንዱ "በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ" የሚል ነው።በዚህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በኋላ እንዳረገ ማመናችንን እንገልጣለን።ይህንን ሃይማኖታችንን ያገኘነውም "የእግዚአብሔር መንፈስ ካለባቸው" ቅዱሳት መጻሕፍት ነው።(2ኛ ጢሞ 3:16)
ቅዱስ ዳዊት "በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" (መዝ 67:33) ቅዱስ ሉቃስ ደግሞ "ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ" (ሉቃ 24:51) ብለውናል።እነዚህም የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነቶች ናቸው።
"ዕርገተ ክርስቶስ በነገረ ማርያም"
#የእመቤታችን ወዳጅ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ" ሲል ያመሰግናታል።ይኸውም ለቃል ርደት(መውረድ (ሰው መሆን) ) ለሥጋ ዕርገት ( ከፍ ማለት (አምላክ መሆን) )ምክንያት ድንግል ማርያም ናት ማለት ነው።ቃል ሥጋ ሲሆን ሥጋም ቃልን በመሆን ከፍ ያለው (ያረገው) በማኅፀነ ድንግል ማርያም ነው።ኋላም ከተነሣ በዐርባኛው ቀን ያረገው ከእመቤታችን ሰው በሆነበት ሥጋ ነው።በዕርገቱ ጊዜ ከእናቱ የነሣው (የተዋሐደው) ሥጋ አልተለየውም።"በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ..." በሚለው ኃይለቃል ውስጥ ያለው "ምሥራቅ" የሚለው ቃልም "ሥጋ ማርያም"ን ያሳያል።ጌታ ፀሐየ ጽድቅ ሆኖ ከእርሷ የወጣባት ምሥራቅ ድንግል ማርያም ናትና።ስለዚህ ኃይለ ቃሉ "በድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ተብሎ ይተረጎማል።
"ዕርገተ ክርስቶስ በአምልኮአችን"
#ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትገለጥበት ትልቁ አምልኮዋ ቅዳሴ ነው።የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ "አሜን" ( አሜን ለሃይማኖት ሲሆን ትክክል/እውነት ማለት ነው) እያለች ከምትናገራቸው ምስክርነቶቿ አንዱ "ነአምን ዕርገተከ ወዳግመ ምጽአተከ" (ዕርገትህን እናምናለን ሁለተኛ መምጣትህንም) የሚል ነው።እንዲሁም ካህኑ "አልዕሉ አልባቢክሙ" (ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ) በማለት ከፍ ከፍ ያለውን አምላካችንን ሲያሳስበን ዲያቆኑ ደግሞ "ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ" ብሎ የጌታን በምሥራቅ ማረግ ያስታውሰናል።ልቡናን ከፍ ከፍ ማድረግም በዓይነ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር ጌታን ሲያርግ መመልከት ፤ በዕዝነ ልቡና የቅዱሳን መላእክቱን ዝማሬ ማድመጥ፤ በአንፈ ልቡና መዓዛ ዕርገቱን ማሽተት ፤ በእግረ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር በደብረ ዘይት መቆም፤በአብራከ ልቡና ለጌታችን መስገድና በዚህ ሁሉ መደሰት ነው።"እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" እንዲል (ሉቃ 24:52)
"ዕርገተ ክርስቶስ በክርስቲያናዊ ሕይወት"
#ጌታችን ወደ ላይ ከፍ ከፍ እንዳለ ክርስትናም ከፍ ከፍ የማለት ሕይወት ነው።ተወዳጅ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ "በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል" (1ኛ ዮሐ 2:6) እንዳለ ጌታችን ከፍ ከፍ እንዳለ እኛም በቅድስና ከፍ ከፍ ልንል ይገባናል።ይህ የቅድስና ሕይወትም ከሥጋ ንጽሕና ወደ ነፍስ ንጽሕና ከነፍስ ንጽሕና ወደ ልቡና ንጽሕና የሚደረግ ጉዞ ነው።ከሁሉ አስቀድመን ግን ከስድብ ወደ ምስጋና፣ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ከቂም ወደ ይቅርታ፣ከዓለም ወደ ቤተክርስቲያን፣ከፍልስፍና ወደ ሃይማኖት፣ከገዛ አጉል እሳቤአችን ወደ እግዚአብሔር ሐሳብ ከፍ ከፍ ልንል ያስፈልገናል!!!
"ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው ፤ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን።" (2ኛ ተሰ 4:17)
መድኃኔዓለም እንዲህ ያለውን የክብር መነጠቅ በቸርነቱ ያድለን !!!
ሰኔ 07/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#በጸሎተ ሃይማኖታችን ከምንመሰክራቸው ምስክርነቶች አንዱ "በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተጻፈ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ" የሚል ነው።በዚህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተነሣ በኋላ እንዳረገ ማመናችንን እንገልጣለን።ይህንን ሃይማኖታችንን ያገኘነውም "የእግዚአብሔር መንፈስ ካለባቸው" ቅዱሳት መጻሕፍት ነው።(2ኛ ጢሞ 3:16)
ቅዱስ ዳዊት "በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" (መዝ 67:33) ቅዱስ ሉቃስ ደግሞ "ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ" (ሉቃ 24:51) ብለውናል።እነዚህም የቅዱሳት መጻሕፍት ምስክርነቶች ናቸው።
"ዕርገተ ክርስቶስ በነገረ ማርያም"
#የእመቤታችን ወዳጅ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ "ከምድር ወደ ሰማይ ለማረግ መሰላል ሆንሽ" ሲል ያመሰግናታል።ይኸውም ለቃል ርደት(መውረድ (ሰው መሆን) ) ለሥጋ ዕርገት ( ከፍ ማለት (አምላክ መሆን) )ምክንያት ድንግል ማርያም ናት ማለት ነው።ቃል ሥጋ ሲሆን ሥጋም ቃልን በመሆን ከፍ ያለው (ያረገው) በማኅፀነ ድንግል ማርያም ነው።ኋላም ከተነሣ በዐርባኛው ቀን ያረገው ከእመቤታችን ሰው በሆነበት ሥጋ ነው።በዕርገቱ ጊዜ ከእናቱ የነሣው (የተዋሐደው) ሥጋ አልተለየውም።"በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ..." በሚለው ኃይለቃል ውስጥ ያለው "ምሥራቅ" የሚለው ቃልም "ሥጋ ማርያም"ን ያሳያል።ጌታ ፀሐየ ጽድቅ ሆኖ ከእርሷ የወጣባት ምሥራቅ ድንግል ማርያም ናትና።ስለዚህ ኃይለ ቃሉ "በድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ" ተብሎ ይተረጎማል።
"ዕርገተ ክርስቶስ በአምልኮአችን"
#ቅድስት ቤተክርስቲያን የምትገለጥበት ትልቁ አምልኮዋ ቅዳሴ ነው።የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ "አሜን" ( አሜን ለሃይማኖት ሲሆን ትክክል/እውነት ማለት ነው) እያለች ከምትናገራቸው ምስክርነቶቿ አንዱ "ነአምን ዕርገተከ ወዳግመ ምጽአተከ" (ዕርገትህን እናምናለን ሁለተኛ መምጣትህንም) የሚል ነው።እንዲሁም ካህኑ "አልዕሉ አልባቢክሙ" (ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ) በማለት ከፍ ከፍ ያለውን አምላካችንን ሲያሳስበን ዲያቆኑ ደግሞ "ወደ ምሥራቅ ተመልከቱ" ብሎ የጌታን በምሥራቅ ማረግ ያስታውሰናል።ልቡናን ከፍ ከፍ ማድረግም በዓይነ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር ጌታን ሲያርግ መመልከት ፤ በዕዝነ ልቡና የቅዱሳን መላእክቱን ዝማሬ ማድመጥ፤ በአንፈ ልቡና መዓዛ ዕርገቱን ማሽተት ፤ በእግረ ልቡና ከሐዋርያቱ ጋር በደብረ ዘይት መቆም፤በአብራከ ልቡና ለጌታችን መስገድና በዚህ ሁሉ መደሰት ነው።"እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ" እንዲል (ሉቃ 24:52)
"ዕርገተ ክርስቶስ በክርስቲያናዊ ሕይወት"
#ጌታችን ወደ ላይ ከፍ ከፍ እንዳለ ክርስትናም ከፍ ከፍ የማለት ሕይወት ነው።ተወዳጅ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ "በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል" (1ኛ ዮሐ 2:6) እንዳለ ጌታችን ከፍ ከፍ እንዳለ እኛም በቅድስና ከፍ ከፍ ልንል ይገባናል።ይህ የቅድስና ሕይወትም ከሥጋ ንጽሕና ወደ ነፍስ ንጽሕና ከነፍስ ንጽሕና ወደ ልቡና ንጽሕና የሚደረግ ጉዞ ነው።ከሁሉ አስቀድመን ግን ከስድብ ወደ ምስጋና፣ከጥላቻ ወደ ፍቅር፣ከቂም ወደ ይቅርታ፣ከዓለም ወደ ቤተክርስቲያን፣ከፍልስፍና ወደ ሃይማኖት፣ከገዛ አጉል እሳቤአችን ወደ እግዚአብሔር ሐሳብ ከፍ ከፍ ልንል ያስፈልገናል!!!
"ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው ፤ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን።" (2ኛ ተሰ 4:17)
መድኃኔዓለም እንዲህ ያለውን የክብር መነጠቅ በቸርነቱ ያድለን !!!
ሰኔ 07/2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ዛሬ #እግዚአብሔር “ኑ፥ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።” (ዘፍ 11፥7) ብሎ ለራሱ በብዙ ቁጥር ተናግሮ ሦስትነቱን ገልጧል።ስለዚህም ቅድስት #ሥላሴ ብለን እናከብራለን።ቅድስት #ሥላሴ ማለትም ልዩ ሦስትነት ማለት ነው።
#እግዚአብሔር ያንጻል #እግዚአብሔር ያፈርሳል
#“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።”( ዘፍ1፥1) በሚለው ቃል የእግዚአብሔርን አናፂነቱን ተረዳን ፤“እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተው።"ዘፍ 11፥8) በሚለው ቃልም የእግዚአብሔር አፍራሽነቱን ዐወቅን።የሰናዖርን ግንብ የገነቡ ሰዎች ዓላማቸው እግዚአብሔርን ከንግሥና ዙፋኑ አውርዶ ለመንገሥ ነበር።
#እነዚህም ቅዱስ #ዳዊት"የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜ በቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል።"(መዝ 2:2-5) ብሎ የተናገረላቸው ዓይነት ሰዎች ናቸው።ዓላማቸውም #የእግዚአብሔር አምላክነቱን (ገዢነቱን) ከላያቸው ላይ መጣል ነው።ነገሩ ግን አስቂኝ ነው።ሰው የማይሆንለትን ነገር ሲሞክር ቂልነቱ ያስቃል።
#የሰው ፍላጎት በአጭሩ #እግዚአብሔርን መሆን ነው።የአዳም ምኞት ፣ የባቢሎን ሰዎች ፍላጎት፣ የአላውያን ነገሥታት ጉጉት ፣ አሁን ያለን ሰዎች ፍላጎትም አምላክ መሆን ነው።አምላክ የመሆን ፍላጎታችን ማሳያዎችም አሉ።መውሰድ #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንሰርቃለን ፤ መግደል #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንገድላለን ፤ መፍረድ #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንፈርዳለን።
#ቅድስት #ሥላሴ በዛሬው ዕለት የባቢሎንን ግንብ እንዳፈረሰ የእኛንም የትዕቢትና የኃጢአት ግንብ በቸርነቱ አፍርሶ ፤ ሰውነታችንን ለእርሱ ማደሪያነት ያንጽልን።
#ጥር #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
#እግዚአብሔር ያንጻል #እግዚአብሔር ያፈርሳል
#“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።”( ዘፍ1፥1) በሚለው ቃል የእግዚአብሔርን አናፂነቱን ተረዳን ፤“እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ ከተማይቱንም መሥራት ተው።"ዘፍ 11፥8) በሚለው ቃልም የእግዚአብሔር አፍራሽነቱን ዐወቅን።የሰናዖርን ግንብ የገነቡ ሰዎች ዓላማቸው እግዚአብሔርን ከንግሥና ዙፋኑ አውርዶ ለመንገሥ ነበር።
#እነዚህም ቅዱስ #ዳዊት"የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜ በቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል።"(መዝ 2:2-5) ብሎ የተናገረላቸው ዓይነት ሰዎች ናቸው።ዓላማቸውም #የእግዚአብሔር አምላክነቱን (ገዢነቱን) ከላያቸው ላይ መጣል ነው።ነገሩ ግን አስቂኝ ነው።ሰው የማይሆንለትን ነገር ሲሞክር ቂልነቱ ያስቃል።
#የሰው ፍላጎት በአጭሩ #እግዚአብሔርን መሆን ነው።የአዳም ምኞት ፣ የባቢሎን ሰዎች ፍላጎት፣ የአላውያን ነገሥታት ጉጉት ፣ አሁን ያለን ሰዎች ፍላጎትም አምላክ መሆን ነው።አምላክ የመሆን ፍላጎታችን ማሳያዎችም አሉ።መውሰድ #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንሰርቃለን ፤ መግደል #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንገድላለን ፤ መፍረድ #የእግዚአብሔር ነው እኛ እንፈርዳለን።
#ቅድስት #ሥላሴ በዛሬው ዕለት የባቢሎንን ግንብ እንዳፈረሰ የእኛንም የትዕቢትና የኃጢአት ግንብ በቸርነቱ አፍርሶ ፤ ሰውነታችንን ለእርሱ ማደሪያነት ያንጽልን።
#ጥር #ሥላሴ / 2017 ዓ.ም
ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በዚህ ዕለት ሐምሌ 7 ቀን #ቅድስት_ሥላሴ በአብርሃም ቤት የገቡበት እና ሣራ ይስሐቅን እንደምትወልድ የተናገረበት ዕለት ነው፡፡
ዳግመኛም በዚህ ዕለት ልደቱ እና ዕረፍቱ በአንድ ቀን የገጠመለት የእመቤታችን ወዳጅ ፣ ኢትዮጲያዊው ቄርሎስ የተባለ የሃይማኖት ጠበቃ ፣ ቅዱስ እና ሊቅ #አባ_ጊዮርግስ_ዘጋስጫ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው።
#ቅድስት_ሥላሴ
አባታችን አብርሃም ከተመሳቀለ ጐዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ መንገደኞችን ዅሉ በእንግድነት እየተቀበለ ሲያስተናግድ ይኖር ነበር፡፡ ጥንተ ጠላታችን ሰይጣን ለተንኮል አያርፍምና ይህንን መልካም ግብሩን ለማሰናክል አሰበ፡፡ አስቦም አልቀረ፤ የተጐዳ ሰው መስሎ ከጐዳና ቆሞ አብርሃም እንግዳ መቀበል እንደ ተወ፤ እርሱ ሊበላ ሊጠጣ ከቤቱ ቢሔድ ራሱን ፈንክቶ፣ ደሙን አፍሶ፣ አጥንቱን ከስክሶ፣ ልብሱን ገፎ እንደ መለሰው ወደ አብርሃም ቤት ለሚሔዱ ሰዎች ይናገር ጀመር፡፡ በዚህ የተነሣም እንግዳ ወደ አብርሃም ቤት አልመጣ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ አብርሃምም ማዕደ እግዚአብሔርን ያለ ምስክር (ያለ እንግዳ) አልመገብም ብሎ ሦስት ቀን ሳይመገብ ጾሙን አደረ፡፡ በሦስተኛው ቀን ይህን ደግነቱን እግዚአብሔር ተመልክቶ በሦስት ሰዎች አምሳል አንድም በሥላሴው (በሦስትነቱ) ከአብርሃም ቤት ገብቷል (ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ፣ 4 ፥32 )፡፡
በኦሪት ዘፍጥረት 18 ፥ 1 -19 ተጽፎ እንደምናገኘው በቀትር ጊዜ አብርሃም በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በሦስት ሰዎች አምሳል በመምሬ አድባር ዛፍ ተገልጦለታል፡፡ አብርሃምም ሦስት ሰዎች ቆመው ባየ ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ወደ እነርሱ ሮጠ፡፡ ወደ ምድርም ሰገደና ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ኾነ ባርያህን አትለፈኝ?›› ብሎ ተማጸነ፡፡ በመቀጠል አብርሃም ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፤ እግራችሁን ታጠቡ፤ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፡፡ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፤ ልባችሁንም ደግፉ፡፡ ከዚያም በኋላ ትሔዳላችሁ፡፡ ስለዚህ ወደ ባርያችሁ መጥታችኋልና›› ሲላቸው እነርሱም ‹‹እንዳልህ አድርግ›› ብለውታል፡፡
ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ጠርቶ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት?›› አለው፡፡ አብርሃምም ከድንኳኑ ውስጥ እንዳለች ነገረው፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች›› ብሎ ለአብርሃም አበሠረው፡፡ ሣራ ይህንን ቃል በሰማች ጊዜ ባለቤቷም አርጅቶ፤ እርሷም የሴቶች ግዳጅ ትቷት ነበርና ‹‹‹ሲያረጁ አምባር ይዋጁ› እንዲሉ ‹‹እስከ ዛሬ ድረስ ቆንጆ ነኝን? ጌታዬ አብርሃምስ ገና ጐረምሳ ነውን?›› ብላ በማሰቧና መውለዷን በመጠራጠሯ ሳቀች፡፡ እግዚአብሔርም ምሥጢሩን በአጽንዖት ለማስረዳትና አስረግጦ ለመንገር አብርሃምን ‹‹ሣራ ለምን ትስቃለች? በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን?›› አለው፡፡ ሣራም ስለፈራች ‹‹አልሳቅሁም›› አለች፡፡ እግዚአብሔርም መሳቋን እንዳወቀባት ከነገራት በኋላ በድጋሜ በዓመቱ ወደ አብርሃም ቤት እንደሚመጣና ሣራ ወንድ ልጅ (ይስሐቅን) እንደምትወልድ አብሥሯቸዋል፡፡
የቅድስት ሥላሴ ረድኤታቸው አይየን!
የቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አማላጅነቱ አትለየን ። ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጺያን ሊለያይ የሚሽቀዳደመውን ዲያብሎስን በመስቀሉ ይምታልን።
©️ ዮቶር ደሳለኝ
#መልካም_በዓል
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተክርስቲያን_ቅድስት@zdk24_5_21_official
ዳግመኛም በዚህ ዕለት ልደቱ እና ዕረፍቱ በአንድ ቀን የገጠመለት የእመቤታችን ወዳጅ ፣ ኢትዮጲያዊው ቄርሎስ የተባለ የሃይማኖት ጠበቃ ፣ ቅዱስ እና ሊቅ #አባ_ጊዮርግስ_ዘጋስጫ ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው።
#ቅድስት_ሥላሴ
አባታችን አብርሃም ከተመሳቀለ ጐዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ መንገደኞችን ዅሉ በእንግድነት እየተቀበለ ሲያስተናግድ ይኖር ነበር፡፡ ጥንተ ጠላታችን ሰይጣን ለተንኮል አያርፍምና ይህንን መልካም ግብሩን ለማሰናክል አሰበ፡፡ አስቦም አልቀረ፤ የተጐዳ ሰው መስሎ ከጐዳና ቆሞ አብርሃም እንግዳ መቀበል እንደ ተወ፤ እርሱ ሊበላ ሊጠጣ ከቤቱ ቢሔድ ራሱን ፈንክቶ፣ ደሙን አፍሶ፣ አጥንቱን ከስክሶ፣ ልብሱን ገፎ እንደ መለሰው ወደ አብርሃም ቤት ለሚሔዱ ሰዎች ይናገር ጀመር፡፡ በዚህ የተነሣም እንግዳ ወደ አብርሃም ቤት አልመጣ አለ፡፡ በዚህ ጊዜ አብርሃምም ማዕደ እግዚአብሔርን ያለ ምስክር (ያለ እንግዳ) አልመገብም ብሎ ሦስት ቀን ሳይመገብ ጾሙን አደረ፡፡ በሦስተኛው ቀን ይህን ደግነቱን እግዚአብሔር ተመልክቶ በሦስት ሰዎች አምሳል አንድም በሥላሴው (በሦስትነቱ) ከአብርሃም ቤት ገብቷል (ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጓሜ፣ 4 ፥32 )፡፡
በኦሪት ዘፍጥረት 18 ፥ 1 -19 ተጽፎ እንደምናገኘው በቀትር ጊዜ አብርሃም በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በሦስት ሰዎች አምሳል በመምሬ አድባር ዛፍ ተገልጦለታል፡፡ አብርሃምም ሦስት ሰዎች ቆመው ባየ ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ወደ እነርሱ ሮጠ፡፡ ወደ ምድርም ሰገደና ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ኾነ ባርያህን አትለፈኝ?›› ብሎ ተማጸነ፡፡ በመቀጠል አብርሃም ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፤ እግራችሁን ታጠቡ፤ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፡፡ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፤ ልባችሁንም ደግፉ፡፡ ከዚያም በኋላ ትሔዳላችሁ፡፡ ስለዚህ ወደ ባርያችሁ መጥታችኋልና›› ሲላቸው እነርሱም ‹‹እንዳልህ አድርግ›› ብለውታል፡፡
ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ጠርቶ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት?›› አለው፡፡ አብርሃምም ከድንኳኑ ውስጥ እንዳለች ነገረው፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች›› ብሎ ለአብርሃም አበሠረው፡፡ ሣራ ይህንን ቃል በሰማች ጊዜ ባለቤቷም አርጅቶ፤ እርሷም የሴቶች ግዳጅ ትቷት ነበርና ‹‹‹ሲያረጁ አምባር ይዋጁ› እንዲሉ ‹‹እስከ ዛሬ ድረስ ቆንጆ ነኝን? ጌታዬ አብርሃምስ ገና ጐረምሳ ነውን?›› ብላ በማሰቧና መውለዷን በመጠራጠሯ ሳቀች፡፡ እግዚአብሔርም ምሥጢሩን በአጽንዖት ለማስረዳትና አስረግጦ ለመንገር አብርሃምን ‹‹ሣራ ለምን ትስቃለች? በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን?›› አለው፡፡ ሣራም ስለፈራች ‹‹አልሳቅሁም›› አለች፡፡ እግዚአብሔርም መሳቋን እንዳወቀባት ከነገራት በኋላ በድጋሜ በዓመቱ ወደ አብርሃም ቤት እንደሚመጣና ሣራ ወንድ ልጅ (ይስሐቅን) እንደምትወልድ አብሥሯቸዋል፡፡
የቅድስት ሥላሴ ረድኤታቸው አይየን!
የቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አማላጅነቱ አትለየን ። ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጺያን ሊለያይ የሚሽቀዳደመውን ዲያብሎስን በመስቀሉ ይምታልን።
©️ ዮቶር ደሳለኝ
#መልካም_በዓል
#ጸልዩ_በእንተ_ቤተክርስቲያን_ቅድስት@zdk24_5_21_official