❝...#ጌታ_ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።❞
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 1
ሰላም ወዳጆች...
እንዴት ነው ?
ዓመቱ እንዴት እየተጠናቀቀ ነው?
እግዚአብሔር ፈቅዶ 2014 ዓ.ም ዘመነ ማርቆስን ለማገባደድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ቀርተውናል ። እስቲ ዘወር ብለን ያለፈውን ጊዜያቶች እንዴት እንዳሳለፍን እንመርምር። መመርመር በጥያቄ ይጀምራል እና ይህንን ልጠይቅ... !
ስንቱን አተረፍንበት.... ?
ስንቱን ከሰርንበት.... ? ለምን ?
ስንቱንን በሚጠቅመን ነገር አሳለፍንበት ...?
ስንቱን በማይጠቅም ነገር አሳለፍንበት.... ? ለምን?
ምን ያህሉን ጊዜ አዲስ ዕውቀት ለመጨመር ተጋንበት ?
ስንት መጽሃፍትን አነበብን ? ስንቱን ኖርነው ?
በዚህ ዓመት ልንፈጽመው #ካቀድነቸው ነገሮች ውስጥ ምን ያህሉን አሳካናቸው ? ምን ያህሉን አላሳካነውም? ለምን ?
ከሁሉም ከሁሉም ግን ወሳኙ ጥያቄ ምን ያህሉን ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰጠነው ? ምንያህሉን ጊዜ ከእግዚብሔር ጋር ተገናኘንበት ? የሚለው ነው ?
በእርግጥ ይህንን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ጊዜ ቢያስፈልገውም እንዲው የግምገማ ጊዜ ቢኖረን ከሚል ወንድማዊ ፍቅር ጠየኩኝ ። በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ግን ለሁሉም ላላሳካነቸው ነገሮች ያሳምንም አያሳምንም ? ይብዛም ይነስም አዕምሮአችን ምክንያት ይሰጠናል ።
#ንግባኬ_ሀበ_ጥንተ_ነገር እንዲል ሊቁ ወደ ቀደመ ነገሬ ስመለስ ከላይ ላሉት ጥያቄዎች ለምን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት አልቻልኩም ብለን ስንጠይቅ መልሱ ወደ አንድ ነገር ያመራናል ።
የጊዜ አጠቃቀም እና ምክንያታዊነት!
ስለ ጊዜ አጠቃቀም በሌላ ርዕስ ብመለስበት ስለሚሻል ስለ ምክንያታዊነት ይህንን ልበል! ቅዱስ መጽሀፍ እንደሚያስተምረው ለየትኛውም ስንፉናችን ምክንያት ሊያድነን አይችልም።
❝እኔ መጥቼ ባልነገርኋቸውስ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ለኃጢአታቸው #ምክንያት የላቸውም።❞ ዮሐንስ 15: 22
ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያስተም ስላደረገው ተዓምር እስራኤላውያን እንዳይሰናከሉ አንድም ለሰው ልጅ ተዐምራቱ ላይ እንዳንሰናከል ምክንያትን ለማስወገድ አንድን ተዐምር በአራት ወንጌላውያን ሲያስመሰከር ሲያጽፍ እንገኘዋለን። ይህም ተዐምር...
• ቅዱስ ማቴዎስ... ቦታው የተመቸ (ሳር እና ለምለም) እንደነበር ይገልጣል። ለምን ይህንን መግለጥ አስፈለገው ቢሉ አይሁዳውያን ቦታው አልተመችንም ስለዚህም አልበላንም እንዳይሉ!
ማቴዎስ 14 :19
ሕዝቡም #በሣር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፥ አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከ፥ እንጀራውንም ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
• ቅዱስ ማርቆስ ደግሞ ቦታው ምድረ በዳ (ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ) እንደነበር ይገልጻል ። ለምን ይህንን ገለጠ ቢሉ ከከተማ ገዝተው አበረከትን ይላሉ እንዳይሉ!
ማርቆስ 8 ፡ 4
ደቀ መዛሙርቱም፦ በዚህ #በምድረ_በዳ እንጀራ ከየት አግኝቶ ሰው እነዚህን ማጥገብ ይችላል? ብለው መለሱለት።
• ቅዱስ ሉቃስ ወቅቱን ይገልጽልናል። መሽቶ እንደነበር ። ተዐምሩን ለምን በቀን አላደረገም ቢሉ በጠዋት ቢያደርገው በልተን መጥተናል ባሉት ነበር በምሳ ቢያደርገው የጠዋቱ አለ ባሉት ነበር ። ስለዚህ አብረው ውለው ማታ አድርጎ ምክንያት አሳጣን።
ሉቃስ 9: 12
❝ቀኑም ይመሽ ጀመር፤ አሥራ ሁለቱም ቀርበው፦ በዚህ በምድረ በዳ ነንና በዙሪያችን ወዳሉ መንደሮችና ገጠሮች ሄደው እንዲያድሩና ምግብ እንዲያገኙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።❞
• ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ አካባቢውን በመግለጽ ይጀምራል። ምክንያት ቢሉ አይሁድ የማንጻት ለማዳ ነበራቸው እና! ሳይታጠቡ አይበሉም ነበር እና !
ዮሐንስ 6: 1
❝ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።❞
ይህ የሚያስተምረን ለየትኛውም ድክመታችን ምክንያት እንደሌለን ነው።
ከምክንያተኝነት በመቀጠል ትልቁ ችግር ከእቅዳችን እግዚአብሔርን ማስወጣት ነው ። ምንም ነገር ስንጀምር ፈቃደ እግዚአብሔርን ካላስቀደምን ጦርነት ሳይጀምር እንደተሸነፈ ወታደር ነን !
ሊቁ እንደተናገረው። " እግዚአብሔር የሌለበት ዕቅድ እና መስመር የሳተ መንገደኛ አንድ ነው " ሁለቱም መድረሻቸው አያታወቅም እና!
እንቀጥላለን... !
መ/ር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
26/12/2014
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 1
ሰላም ወዳጆች...
እንዴት ነው ?
ዓመቱ እንዴት እየተጠናቀቀ ነው?
እግዚአብሔር ፈቅዶ 2014 ዓ.ም ዘመነ ማርቆስን ለማገባደድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ቀርተውናል ። እስቲ ዘወር ብለን ያለፈውን ጊዜያቶች እንዴት እንዳሳለፍን እንመርምር። መመርመር በጥያቄ ይጀምራል እና ይህንን ልጠይቅ... !
ስንቱን አተረፍንበት.... ?
ስንቱን ከሰርንበት.... ? ለምን ?
ስንቱንን በሚጠቅመን ነገር አሳለፍንበት ...?
ስንቱን በማይጠቅም ነገር አሳለፍንበት.... ? ለምን?
ምን ያህሉን ጊዜ አዲስ ዕውቀት ለመጨመር ተጋንበት ?
ስንት መጽሃፍትን አነበብን ? ስንቱን ኖርነው ?
በዚህ ዓመት ልንፈጽመው #ካቀድነቸው ነገሮች ውስጥ ምን ያህሉን አሳካናቸው ? ምን ያህሉን አላሳካነውም? ለምን ?
ከሁሉም ከሁሉም ግን ወሳኙ ጥያቄ ምን ያህሉን ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰጠነው ? ምንያህሉን ጊዜ ከእግዚብሔር ጋር ተገናኘንበት ? የሚለው ነው ?
በእርግጥ ይህንን ጥያቄ ሙሉ ለሙሉ ለመመለስ ጊዜ ቢያስፈልገውም እንዲው የግምገማ ጊዜ ቢኖረን ከሚል ወንድማዊ ፍቅር ጠየኩኝ ። በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ግን ለሁሉም ላላሳካነቸው ነገሮች ያሳምንም አያሳምንም ? ይብዛም ይነስም አዕምሮአችን ምክንያት ይሰጠናል ።
#ንግባኬ_ሀበ_ጥንተ_ነገር እንዲል ሊቁ ወደ ቀደመ ነገሬ ስመለስ ከላይ ላሉት ጥያቄዎች ለምን ሙሉ ለሙሉ ማሳካት አልቻልኩም ብለን ስንጠይቅ መልሱ ወደ አንድ ነገር ያመራናል ።
የጊዜ አጠቃቀም እና ምክንያታዊነት!
ስለ ጊዜ አጠቃቀም በሌላ ርዕስ ብመለስበት ስለሚሻል ስለ ምክንያታዊነት ይህንን ልበል! ቅዱስ መጽሀፍ እንደሚያስተምረው ለየትኛውም ስንፉናችን ምክንያት ሊያድነን አይችልም።
❝እኔ መጥቼ ባልነገርኋቸውስ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ለኃጢአታቸው #ምክንያት የላቸውም።❞ ዮሐንስ 15: 22
ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲያስተም ስላደረገው ተዓምር እስራኤላውያን እንዳይሰናከሉ አንድም ለሰው ልጅ ተዐምራቱ ላይ እንዳንሰናከል ምክንያትን ለማስወገድ አንድን ተዐምር በአራት ወንጌላውያን ሲያስመሰከር ሲያጽፍ እንገኘዋለን። ይህም ተዐምር...
• ቅዱስ ማቴዎስ... ቦታው የተመቸ (ሳር እና ለምለም) እንደነበር ይገልጣል። ለምን ይህንን መግለጥ አስፈለገው ቢሉ አይሁዳውያን ቦታው አልተመችንም ስለዚህም አልበላንም እንዳይሉ!
ማቴዎስ 14 :19
ሕዝቡም #በሣር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፥ አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከ፥ እንጀራውንም ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
• ቅዱስ ማርቆስ ደግሞ ቦታው ምድረ በዳ (ከከተማ ወጣ ያለ ስፍራ) እንደነበር ይገልጻል ። ለምን ይህንን ገለጠ ቢሉ ከከተማ ገዝተው አበረከትን ይላሉ እንዳይሉ!
ማርቆስ 8 ፡ 4
ደቀ መዛሙርቱም፦ በዚህ #በምድረ_በዳ እንጀራ ከየት አግኝቶ ሰው እነዚህን ማጥገብ ይችላል? ብለው መለሱለት።
• ቅዱስ ሉቃስ ወቅቱን ይገልጽልናል። መሽቶ እንደነበር ። ተዐምሩን ለምን በቀን አላደረገም ቢሉ በጠዋት ቢያደርገው በልተን መጥተናል ባሉት ነበር በምሳ ቢያደርገው የጠዋቱ አለ ባሉት ነበር ። ስለዚህ አብረው ውለው ማታ አድርጎ ምክንያት አሳጣን።
ሉቃስ 9: 12
❝ቀኑም ይመሽ ጀመር፤ አሥራ ሁለቱም ቀርበው፦ በዚህ በምድረ በዳ ነንና በዙሪያችን ወዳሉ መንደሮችና ገጠሮች ሄደው እንዲያድሩና ምግብ እንዲያገኙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።❞
• ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ አካባቢውን በመግለጽ ይጀምራል። ምክንያት ቢሉ አይሁድ የማንጻት ለማዳ ነበራቸው እና! ሳይታጠቡ አይበሉም ነበር እና !
ዮሐንስ 6: 1
❝ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ ተሻገረ፤ እርሱም የጥብርያዶስ ባሕር ነው።❞
ይህ የሚያስተምረን ለየትኛውም ድክመታችን ምክንያት እንደሌለን ነው።
ከምክንያተኝነት በመቀጠል ትልቁ ችግር ከእቅዳችን እግዚአብሔርን ማስወጣት ነው ። ምንም ነገር ስንጀምር ፈቃደ እግዚአብሔርን ካላስቀደምን ጦርነት ሳይጀምር እንደተሸነፈ ወታደር ነን !
ሊቁ እንደተናገረው። " እግዚአብሔር የሌለበት ዕቅድ እና መስመር የሳተ መንገደኛ አንድ ነው " ሁለቱም መድረሻቸው አያታወቅም እና!
እንቀጥላለን... !
መ/ር ዲ/ን እስጢፋኖስ ደ.
26/12/2014
.....የቀጠለ
❝...#ጌታ_ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።❞
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 2
ሰላም ወዳጆች ? ትላንት በክፍል 1 ቆያታችን እያገባደድን እየመጣን ስላለው ዓመት አጭር የግምገማ እና ለምን አላሳካነውም ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ጀምረን ነበር ።
ምክንያተኝነትን እና ምክንያትን ለዓላማ እንዲሁ ለ መንፈሳዊ እድገት መቀጨጭ ዋና አስተዋጽዖ እንዳለው በግርድፉ ተመልክተን ነበር ።
ዛሬም በዚህ በክፍል ሁለት አንድ አንድ ነገር እንነገራለን ።
ዓመቱን እንዴት እንዳሳለፍን ለራሳችን ስንጠይቅ ብዙ ነገሮች በአእምሯችን እንደተመላለሱ ለመገመት ሊቅነትን አይጠይቅም ። ዋናው ነገር ግን እርሱ አይደለም ።
መልሶቹ ውጫዊው አጋደለ ወይስ ውስጣዊው???
ወደ ሌላ ወይስ ወደራሳችን ?
ወደ ሰፊው ዓለም ወይስ ወደ ራሳችን ዓለም ?
መልሱ ወደ ወጪ ካመዘነ አሁንም ደግመን የምንጠይቅበት ሰዐት ነው ። ምክንያቱም መልሱን አላገኘነውም ! አለቀ።
ብዙ ጊዜ የችግራችን (መንፈሳዊ ይሁን ዓለማዊ) መንስኤ ውጫዊ እንደሆነ ካሰብን ውጫዊ መፍትሔ ስንፈልግለት እንደ ባዘንን ሳንንድን ሌላ የተሰጠንን ጊዜ እናባክናለን ። ቅዱሱ መጽሃፍ ❝...የመዳን ቀን አሁን ነው።❞ 2ኛ ቆሮ 6: 2 ሲል አሁን የመለወጫ የመወሰኛ ጊዜ ነው እያለን እንደሆነ ልብ ይሏል።
ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው
❝ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ #ምክንያትን ከሚፈልጉቱ #ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።❞
—2ኛ ቆሮ 11: 12
ምክንያተኝነትን እያስወገድን ራሳችንን መመልከት ያስፈልጋል። ሌላው ብዙ ስንጠይቅ መራቀቅን ለጊዜው እያስቀመጥን ቢሆን ደግሞ መልካም ያደርገዋል ።
ሁለት የፍልስፉና መጽሀፍ ያነበበ ወዳጄ" ሰላም ነው?" ስለው የመለስልኝ መልስ ፈገግ ቢያሰኘኝ ነው ይህን ማለቴ !
ጓደኛዬ :- ውስጣዊ ነው ውጫዊ ???
በገድለ አቡነ ተክለሃይማኖት ያለች ልትራቀቅ ወድዳ ፍዳ ያመጣች አንዲት መነኩሲት ሰው ላስታውሳት። አባታችን ጸሀይ ዘኢትዮጲያ አቡነ ተክለሃይማኖት በደብረሊባኖስ በነበሩበት ወቅት አራዊት እየመጡ የልጆቻቸውን አዝመራ እየበሉ አስቸገሯቸው ። ልጆቹም ሄደው " አባታችን! እንስሳት አራዊት አትክልታችንን እየበሉ አስቸገሩን " አሏቸው።
ቅዱስ አባታችንም "ልጆቼ ተውአቸው ። እኛ ወደ ጫካ መጣንባቸው እንጂ እነርሱ አልመጡብንም" ሲሉ መለሱላቸው ።
እንዲህ ሆነው ሳለ ከዕለታት በአንድ ቀን አንዲት አረጋዊት መናኝ ስተመገብ አንድ ዝንጀሮ መጥቶ በጥፊ ጠርቅሞ ቀምቷት በላ ። አባታችንም ይህንን አይተው :- " የተሰጡትን ትቶ ሌላ ያልተሰጡትን መሻት የያዙትን ያሳጣል። እኔ በዱር የተዘራውን ትበሉ ዘንድ ብፈቅድ ከሰው እጅ እየቀማችሁ መብላት ጀመራችሁ?" ብለው "ወንጌልን በምሰክለት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አፋችሁን የታሰረ ይሁን! " በቃለ ማእሰር ዘጓቸው ። ከዚያን ቀን ጀምሮ መብላት ተሳናቸው ።
በስተመጨረሻም ሩጫቸውን ጨርሰው ሊያርፉ ሲሉ ልጆቻቸው ጠርተው ሲሰናበቱ መረቋቸው። በዚህ ጊዜ ያች ሴት ልትራቀቅ ወድዳ " አባቴ በጸሎቶ ያሰሩትም ይፍቱ " ብላ ጠየቀች። እርሳቸውም " የታሰረውም ይፈቱ " ሲሉ ዝንጀሮውም አብሮ ተፈታ ። በዚህም ከቀደመው የበዛውን አጠፉ።
ስናጠቃልለው በነገርም ያለ ነገርም # አትራቀቅ ...!
እንቀጥላለን ።
❝...#ጌታ_ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያንን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።❞
ያዕቆብ 4: 15
ክፍል 2
ሰላም ወዳጆች ? ትላንት በክፍል 1 ቆያታችን እያገባደድን እየመጣን ስላለው ዓመት አጭር የግምገማ እና ለምን አላሳካነውም ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ጀምረን ነበር ።
ምክንያተኝነትን እና ምክንያትን ለዓላማ እንዲሁ ለ መንፈሳዊ እድገት መቀጨጭ ዋና አስተዋጽዖ እንዳለው በግርድፉ ተመልክተን ነበር ።
ዛሬም በዚህ በክፍል ሁለት አንድ አንድ ነገር እንነገራለን ።
ዓመቱን እንዴት እንዳሳለፍን ለራሳችን ስንጠይቅ ብዙ ነገሮች በአእምሯችን እንደተመላለሱ ለመገመት ሊቅነትን አይጠይቅም ። ዋናው ነገር ግን እርሱ አይደለም ።
መልሶቹ ውጫዊው አጋደለ ወይስ ውስጣዊው???
ወደ ሌላ ወይስ ወደራሳችን ?
ወደ ሰፊው ዓለም ወይስ ወደ ራሳችን ዓለም ?
መልሱ ወደ ወጪ ካመዘነ አሁንም ደግመን የምንጠይቅበት ሰዐት ነው ። ምክንያቱም መልሱን አላገኘነውም ! አለቀ።
ብዙ ጊዜ የችግራችን (መንፈሳዊ ይሁን ዓለማዊ) መንስኤ ውጫዊ እንደሆነ ካሰብን ውጫዊ መፍትሔ ስንፈልግለት እንደ ባዘንን ሳንንድን ሌላ የተሰጠንን ጊዜ እናባክናለን ። ቅዱሱ መጽሃፍ ❝...የመዳን ቀን አሁን ነው።❞ 2ኛ ቆሮ 6: 2 ሲል አሁን የመለወጫ የመወሰኛ ጊዜ ነው እያለን እንደሆነ ልብ ይሏል።
ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው
❝ነገር ግን በዚያ በሚመኩበት እንደ እኛ ሆነው ሊገኙ፥ #ምክንያትን ከሚፈልጉቱ #ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።❞
—2ኛ ቆሮ 11: 12
ምክንያተኝነትን እያስወገድን ራሳችንን መመልከት ያስፈልጋል። ሌላው ብዙ ስንጠይቅ መራቀቅን ለጊዜው እያስቀመጥን ቢሆን ደግሞ መልካም ያደርገዋል ።
ሁለት የፍልስፉና መጽሀፍ ያነበበ ወዳጄ" ሰላም ነው?" ስለው የመለስልኝ መልስ ፈገግ ቢያሰኘኝ ነው ይህን ማለቴ !
ጓደኛዬ :- ውስጣዊ ነው ውጫዊ ???
በገድለ አቡነ ተክለሃይማኖት ያለች ልትራቀቅ ወድዳ ፍዳ ያመጣች አንዲት መነኩሲት ሰው ላስታውሳት። አባታችን ጸሀይ ዘኢትዮጲያ አቡነ ተክለሃይማኖት በደብረሊባኖስ በነበሩበት ወቅት አራዊት እየመጡ የልጆቻቸውን አዝመራ እየበሉ አስቸገሯቸው ። ልጆቹም ሄደው " አባታችን! እንስሳት አራዊት አትክልታችንን እየበሉ አስቸገሩን " አሏቸው።
ቅዱስ አባታችንም "ልጆቼ ተውአቸው ። እኛ ወደ ጫካ መጣንባቸው እንጂ እነርሱ አልመጡብንም" ሲሉ መለሱላቸው ።
እንዲህ ሆነው ሳለ ከዕለታት በአንድ ቀን አንዲት አረጋዊት መናኝ ስተመገብ አንድ ዝንጀሮ መጥቶ በጥፊ ጠርቅሞ ቀምቷት በላ ። አባታችንም ይህንን አይተው :- " የተሰጡትን ትቶ ሌላ ያልተሰጡትን መሻት የያዙትን ያሳጣል። እኔ በዱር የተዘራውን ትበሉ ዘንድ ብፈቅድ ከሰው እጅ እየቀማችሁ መብላት ጀመራችሁ?" ብለው "ወንጌልን በምሰክለት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አፋችሁን የታሰረ ይሁን! " በቃለ ማእሰር ዘጓቸው ። ከዚያን ቀን ጀምሮ መብላት ተሳናቸው ።
በስተመጨረሻም ሩጫቸውን ጨርሰው ሊያርፉ ሲሉ ልጆቻቸው ጠርተው ሲሰናበቱ መረቋቸው። በዚህ ጊዜ ያች ሴት ልትራቀቅ ወድዳ " አባቴ በጸሎቶ ያሰሩትም ይፍቱ " ብላ ጠየቀች። እርሳቸውም " የታሰረውም ይፈቱ " ሲሉ ዝንጀሮውም አብሮ ተፈታ ። በዚህም ከቀደመው የበዛውን አጠፉ።
ስናጠቃልለው በነገርም ያለ ነገርም # አትራቀቅ ...!
እንቀጥላለን ።
#ጌታ ሆይ የአንተን ነገር ከመናገር አለመናገር የበለጠ ገላጭ ነው።ከዝምታም ዕንባ የበለጠ ገላጭ ነው።እስከ መጨረሻው አምላክነትህን የገለጥክላቸው አይሁድ በመቃብርህ ወታደሮችን ቢያኖሩ ሞትን ገድለህ በሥልጣንህ የተነሣኸው ሆይ፤እስከ መጨረሻው ወድደህ (ዮሐ 13:1) የሰውን የመጨረሻ ሥልጣን (ልጅነትን) (ዮሐ1:12) የሰጠኸኝን እኔን ዙሪያን የሚዞረኝን ጠላት(1ኛ ጴጥ 5:8) በትንሣኤህ ብርሃን ድል ንሣልኝ!!!
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!!!በዓሉን የ "የፊተኛውን ትንሣኤ" (ራእይ 20:6) የምንነሣበት ያድርግልን!!! አሜን!!!
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!!!በዓሉን የ "የፊተኛውን ትንሣኤ" (ራእይ 20:6) የምንነሣበት ያድርግልን!!! አሜን!!!
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
እመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እንደ ልጇ ተነሥታ ዐርጋለች።"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት"(መዝ 131:8) በማለት ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት የጌታችንና የእናቱን የእመቤታችንን ትንሣኤ አስተባብሮ ተናግሯል።"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ" ብሎ የጌታን "አንተና የመቅደስህ ታቦት" በማለት ጌታችን ብቻ ሳይሆን እናቱም እንደምትነሣ በእውነት ተነበየ።
#ኋላ ጻድቃን የሚቆሙትን የቀኝ ቁመት እመቤታችን ዛሬ ቆማዋለች።"በወርቅ ልብስ ተሸፋፍና ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንዳለ አባቷ ቅዱስ ዳዊት።
#ልጇ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ኋላ ለጻድቃን የሚያወርሳቸውን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን" (1ኛ ቆሮ 2:9) ዛሬ ለእናቱ አውርሷታል።
ለነገሩ ራሷ መንግሥተ ሰማያት ናት።ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ንጉሠ ሰማያት ወምድር ማኅፀኗን መናገሻ አድርጎ ነግሦባታልና።
#ልጇ "ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።"(ዮሐ14:3) እንዳለ እርሷም እርሷ ባለችበት እንሆን ዘንድ ከልጇ ታማልደናለች።ማርያም ማለት መርኅ ለመንግሥተ ሰማያት (በቃልኪዳኗ በአማላጅነቷ ረድታ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ) ማለት ነውና።
#ጌታ መጋቢት 27 በመስቀል ላይ ሞቶ መጋቢት 29 በሦስተኛው ቀን እንደተነሣ እመቤታችንም በጥር 21 ዐርፋ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ በነሐሴ 14 ቀን በጌቴሴማኒ ተቀብራ በነሐሴ 16 ቀን በክብር፣በይባቤ መላእክት ተነሥታ ዐርጋለች።
#አይ የሞተ አይነሣም ለምትሉ አባታችን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን በመንፈስ እንጠራዋለን "ነገር ግን ሰው፤ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም።"(1ኛ ቆሮ 15:35) ብሎ ይዘልፍናል።
#ተነሥቶ ወደ ሰማይ አይወጣም የሚል ቢኖር ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን በሃይማኖት እንጠራዋለን፤እንዴትም ወደ ሰማይ እንደወጣ እንጠይቀዋለን።"ሲሄዱም እያዘገሙም ሲጫወቱ፤ እነሆ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።”(2ኛ ነገ 2:11)
ሞቶ ተነሥቶ ያረገ የለም የሚል ማንም ቢኖር ዳግመኛ ቅዱስ ጳውሎስ
"ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፤ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።"(1ኛ ተሰ 4:16-17) ሲል ይነግርልናል።
#አስተውሉ ያቀረብነው ማስረጃ ጻድቃንን የሚመለከት ነው።ጻድቃን እንዲህ ከከበሩ የጻድቃን እናታቸው የአምላክ እናት ቅደስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምማ ክብሯ ምን ያህል ይሆን !!!!!!!!???
እኛስ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም "አሕዛብ ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናመስግናት" እንላለን!!!
ነሐሴ ኪዳነምሕረት 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ኋላ ጻድቃን የሚቆሙትን የቀኝ ቁመት እመቤታችን ዛሬ ቆማዋለች።"በወርቅ ልብስ ተሸፋፍና ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንዳለ አባቷ ቅዱስ ዳዊት።
#ልጇ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ኋላ ለጻድቃን የሚያወርሳቸውን "ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀውን" (1ኛ ቆሮ 2:9) ዛሬ ለእናቱ አውርሷታል።
ለነገሩ ራሷ መንግሥተ ሰማያት ናት።ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ንጉሠ ሰማያት ወምድር ማኅፀኗን መናገሻ አድርጎ ነግሦባታልና።
#ልጇ "ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ።"(ዮሐ14:3) እንዳለ እርሷም እርሷ ባለችበት እንሆን ዘንድ ከልጇ ታማልደናለች።ማርያም ማለት መርኅ ለመንግሥተ ሰማያት (በቃልኪዳኗ በአማላጅነቷ ረድታ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ) ማለት ነውና።
#ጌታ መጋቢት 27 በመስቀል ላይ ሞቶ መጋቢት 29 በሦስተኛው ቀን እንደተነሣ እመቤታችንም በጥር 21 ዐርፋ ገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ በነሐሴ 14 ቀን በጌቴሴማኒ ተቀብራ በነሐሴ 16 ቀን በክብር፣በይባቤ መላእክት ተነሥታ ዐርጋለች።
#አይ የሞተ አይነሣም ለምትሉ አባታችን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስን በመንፈስ እንጠራዋለን "ነገር ግን ሰው፤ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም።"(1ኛ ቆሮ 15:35) ብሎ ይዘልፍናል።
#ተነሥቶ ወደ ሰማይ አይወጣም የሚል ቢኖር ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን በሃይማኖት እንጠራዋለን፤እንዴትም ወደ ሰማይ እንደወጣ እንጠይቀዋለን።"ሲሄዱም እያዘገሙም ሲጫወቱ፤ እነሆ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ።”(2ኛ ነገ 2:11)
ሞቶ ተነሥቶ ያረገ የለም የሚል ማንም ቢኖር ዳግመኛ ቅዱስ ጳውሎስ
"ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤
ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፤ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።"(1ኛ ተሰ 4:16-17) ሲል ይነግርልናል።
#አስተውሉ ያቀረብነው ማስረጃ ጻድቃንን የሚመለከት ነው።ጻድቃን እንዲህ ከከበሩ የጻድቃን እናታቸው የአምላክ እናት ቅደስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምማ ክብሯ ምን ያህል ይሆን !!!!!!!!???
እኛስ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም "አሕዛብ ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናመስግናት" እንላለን!!!
ነሐሴ ኪዳነምሕረት 2016 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ