❤ሁሉ አንተን ተስፋ ያደርጋሉ❤ (መዝ103፥27)
#ፍጥረት ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል።ምርጫ አይደለም የህልውና ጉዳይ እንጂ።በደመነፍስ ሕያዋን ሆነው የሚኖሩት እንስሳት፣አራዊት፣አዋዕፍ፣ዓሦችና አንበሪዎች እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ ተስፋ ያደርጉታል።እርሱም ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸዋል።ከቸር እጆቹ ጠግበው ያመሰግኑታል።
#ሰውም እንደ መላእክት ሁሉ "ተስፋ" የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።ተስፋውም በሕግ ቃልኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው።“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።”(ዘፍ 2፥17) ሲል ጌታ ለሰው ማዘዙ የሰው የሕይወት ተስፋው ሕጉን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዳል።
#ኋላም በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት የተሰጠው “ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።” (ዘጸ 20፥6) የሚለው ቃል ከላይ ያነሣነውን ሐሳብ ያጠናክረዋል።
#በእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተወደደ ሰው የሚባል ፍጡር ለሕይወቱ የተሰጠውን ሕግ አፍርሶ ቢበድል እንኳን ይቅር የመባል ተስፋ አለው። ስለዚህ የሚተማመነው "በእግዚአብሔር ምሕረት" ላይ እንጂ በራሱ ሕግ የመጠበቅ ብቃት ላይ አይሆንም።
#ተስፋ ቆርጫለሁ
#የሚለው ድምፅ እዚህና እዚያ ይሰማል።ተስፋ ማለት እግዚአብሔር ከሆነ ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት እግዚአብሔርን ትቼአለሁ ማለት ይሆናል።ተስፋ ለመቁረጥ ተስፋ ማድረግ ያስፈልጋል።ሰው ተስፋ የሚያደርጋቸው ጊዜአዊ ነገሮች ከእውነተኛ ተስፋው ከእግዚአብሔር ጋር ይምታቱበትና፤ያልተሳኩ እንደሆነ
ተስፋ ቆረጥሁ ይላል።መማርን፣አንድ ቦታ ተቀጥሮ መሥራትን፣እገሌን ወይ እገሊትን ማግባትን፣ልጆች መውለድን፣ባህር ማዶ ተሻግሮ መኖርን ወ.ዘ.ተ።
#አሁንስ ደከመኝ፣ታከትኩ፣ከዚህ በላይስ አልሄድም፣
በቃኝ ... የሚሉ ንግግሮች ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች አለመሳካት የሚነገሩ ናቸው።"እናንተ ስለፈለጋችሁ የሚሆን ነገር የለም፤ሆኑ አልሆኑ የእግረ መንገድ ጉዳዮች ናቸው።እነዚህ ጉዳዮች እንደ ሕፃናት ማቆያዎች (Day cares) ናቸው።የተፈጠራችሁላቸው ዓላማዎች አይደሉም።" እያለ ሕፃንነታችንን እየነገረን ከሆነስ!? "ፈቃድህ ይሁን" ብለን በፈቃዱ ሲከለክለን ማዘን አይገባም።
#ኑሮው!!! ኧረ ውድነቱ!!! "እግዚአብሔር ሆይ ወዴት ነህ???" "አንተን በማኖር ግብር ነኝ" ይልሃላ።ወይ ግሩም እስከዛሬ ታዲያ በኑሮ ርካሽነት ነበር እንዴ የኖርነው!?በእኔ ዕድሜ ሳውቅ በየጊዜው "ኑሮ ተወደደ" ነው የሚባለው።ሲወደድ እንጂ ሲረክስ ያየሁት ነገር የለም (ከሰው(ከእኔ) በቀር 😭)።ግን በቸርነቱ አለን!!!ግሩም ነው መቼስ!!!
#ለነፍሳችን ለማደር ከኃጢአት ጋር በምናደርገው ትግልም ተመሳሳዩ ነገር ይገጥመናል።"ከዚህ በኋላ ይህንን ያህል በድለህ እግዚአብሔር ይቅር የሚልህ መሰለህ" የሚል ሐሳብ በኅሊናህ ሲመጣ "አዎን ይቅር ይለኛል" በለው።ገድለህ "አዎን"፤አመንዝረህ "አዎን"፤ዘሙተህ "አዎን"፤ሰርቀህ "አዎን"፤"ዋሽተህ" አዎን!!!
#ታዲያ የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?
#ቅዱስ ዳዊት “መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም።”(መዝ 76፥19) ሲል የእግዚአብሔር አሠረ ፍትሑ (የፍርዱ መንገድ) እንደማይታወቅ ተናግሯል።ቅዱስ ጳውሎስም “የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።”(ሮሜ 11 ፥ 33) በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ አይመረመሬነት ገልጧል።ስለዚህ "የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "በራሱ ዘንድ ነው" የሚል ነው።
#ይህንን ሁሉ አጥፈተህማ እግዚአብሔር ሳይቀጣህ አይቀርም" የሚል ድምፅ ኅሊናህ ውስጥ ሲመላለስ፤"እግዚአብሔር ደግ አባቴ ነውና በደንብ ይቅጣኝ፤አንዴ አይደለም መቶ ጊዜ ይቅጣኝ።ብቻ ለአንተ ለከይሲው አሳልፎ አይሰጠኝ።እንኳን የእኔ የአንዱ በደል ከአዳም ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚሠራው ኃጢአት የደጉ አባቴን የእግዚአብሔርን አንዲቱን የምሕረት ጠብታ አያህልም!!!" በለው። እንዲህ ብለን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እግዚአብሔር ደስ ይለዋል።ቁጣውን ሁሉ ይተወዋል።ሰው ራሱ ላይ ከልቡ ሲፈርድ እግዚአብሔር ፍርዱን ይተውለታል!!!
“እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ ጽድቅንም ይወድዳል፤ ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።”(መዝ 11፥7) እንዳለ መዝሙረኛው በጽድቅ ራሳችን ላይ ፈርደን፤በልብ ቅንነት ራሳችንን ጻድቅ ለሆነ እግዚአብሔር ስንሰጥ፤እግዚአብሔር ደግሞ የምሕረት ፊቱን ያሳየናል።ይህንንም በልባችን በሚመላብን ፍጹም ሰላምና ደስታ እናውቃለን!!!
"#ሳለ #መድኃኔዓለም" የምወዳት የእናቶቼ ብሂል ናት።እውነትም "#ሳለ #መድኃኔዓለም" #አምላከ #ተክለሃይማኖት!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 13/2017 ዓ.ም
#ፍጥረት ሁሉ የፈጠረው እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል።ምርጫ አይደለም የህልውና ጉዳይ እንጂ።በደመነፍስ ሕያዋን ሆነው የሚኖሩት እንስሳት፣አራዊት፣አዋዕፍ፣ዓሦችና አንበሪዎች እርሱ እግዚአብሔር ባወቀ ተስፋ ያደርጉታል።እርሱም ምግባቸውን በየጊዜው ይሰጣቸዋል።ከቸር እጆቹ ጠግበው ያመሰግኑታል።
#ሰውም እንደ መላእክት ሁሉ "ተስፋ" የተሰጠው ታላቅ ፍጡር ነው።ተስፋውም በሕግ ቃልኪዳን ላይ የተመሠረተ ነው።“ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና።”(ዘፍ 2፥17) ሲል ጌታ ለሰው ማዘዙ የሰው የሕይወት ተስፋው ሕጉን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያስረዳል።
#ኋላም በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት የተሰጠው “ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።” (ዘጸ 20፥6) የሚለው ቃል ከላይ ያነሣነውን ሐሳብ ያጠናክረዋል።
#በእግዚአብሔር ታላቅ ፍቅር የተወደደ ሰው የሚባል ፍጡር ለሕይወቱ የተሰጠውን ሕግ አፍርሶ ቢበድል እንኳን ይቅር የመባል ተስፋ አለው። ስለዚህ የሚተማመነው "በእግዚአብሔር ምሕረት" ላይ እንጂ በራሱ ሕግ የመጠበቅ ብቃት ላይ አይሆንም።
#ተስፋ ቆርጫለሁ
#የሚለው ድምፅ እዚህና እዚያ ይሰማል።ተስፋ ማለት እግዚአብሔር ከሆነ ተስፋ ቆርጫለሁ ማለት እግዚአብሔርን ትቼአለሁ ማለት ይሆናል።ተስፋ ለመቁረጥ ተስፋ ማድረግ ያስፈልጋል።ሰው ተስፋ የሚያደርጋቸው ጊዜአዊ ነገሮች ከእውነተኛ ተስፋው ከእግዚአብሔር ጋር ይምታቱበትና፤ያልተሳኩ እንደሆነ
ተስፋ ቆረጥሁ ይላል።መማርን፣አንድ ቦታ ተቀጥሮ መሥራትን፣እገሌን ወይ እገሊትን ማግባትን፣ልጆች መውለድን፣ባህር ማዶ ተሻግሮ መኖርን ወ.ዘ.ተ።
#አሁንስ ደከመኝ፣ታከትኩ፣ከዚህ በላይስ አልሄድም፣
በቃኝ ... የሚሉ ንግግሮች ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች አለመሳካት የሚነገሩ ናቸው።"እናንተ ስለፈለጋችሁ የሚሆን ነገር የለም፤ሆኑ አልሆኑ የእግረ መንገድ ጉዳዮች ናቸው።እነዚህ ጉዳዮች እንደ ሕፃናት ማቆያዎች (Day cares) ናቸው።የተፈጠራችሁላቸው ዓላማዎች አይደሉም።" እያለ ሕፃንነታችንን እየነገረን ከሆነስ!? "ፈቃድህ ይሁን" ብለን በፈቃዱ ሲከለክለን ማዘን አይገባም።
#ኑሮው!!! ኧረ ውድነቱ!!! "እግዚአብሔር ሆይ ወዴት ነህ???" "አንተን በማኖር ግብር ነኝ" ይልሃላ።ወይ ግሩም እስከዛሬ ታዲያ በኑሮ ርካሽነት ነበር እንዴ የኖርነው!?በእኔ ዕድሜ ሳውቅ በየጊዜው "ኑሮ ተወደደ" ነው የሚባለው።ሲወደድ እንጂ ሲረክስ ያየሁት ነገር የለም (ከሰው(ከእኔ) በቀር 😭)።ግን በቸርነቱ አለን!!!ግሩም ነው መቼስ!!!
#ለነፍሳችን ለማደር ከኃጢአት ጋር በምናደርገው ትግልም ተመሳሳዩ ነገር ይገጥመናል።"ከዚህ በኋላ ይህንን ያህል በድለህ እግዚአብሔር ይቅር የሚልህ መሰለህ" የሚል ሐሳብ በኅሊናህ ሲመጣ "አዎን ይቅር ይለኛል" በለው።ገድለህ "አዎን"፤አመንዝረህ "አዎን"፤ዘሙተህ "አዎን"፤ሰርቀህ "አዎን"፤"ዋሽተህ" አዎን!!!
#ታዲያ የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?
#ቅዱስ ዳዊት “መንገድህ በባህር ውስጥ ነው፥ ፍለጋህም በብዙ ውኆች ነው፥ አረማመድህም አልታወቀም።”(መዝ 76፥19) ሲል የእግዚአብሔር አሠረ ፍትሑ (የፍርዱ መንገድ) እንደማይታወቅ ተናግሯል።ቅዱስ ጳውሎስም “የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።”(ሮሜ 11 ፥ 33) በማለት የእግዚአብሔርን ፍርድ አይመረመሬነት ገልጧል።ስለዚህ "የእግዚአብሔር ፍርድ ወዴት አለ?" ለሚለው ጥያቄ መልሱ "በራሱ ዘንድ ነው" የሚል ነው።
#ይህንን ሁሉ አጥፈተህማ እግዚአብሔር ሳይቀጣህ አይቀርም" የሚል ድምፅ ኅሊናህ ውስጥ ሲመላለስ፤"እግዚአብሔር ደግ አባቴ ነውና በደንብ ይቅጣኝ፤አንዴ አይደለም መቶ ጊዜ ይቅጣኝ።ብቻ ለአንተ ለከይሲው አሳልፎ አይሰጠኝ።እንኳን የእኔ የአንዱ በደል ከአዳም ጀምሮ እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚሠራው ኃጢአት የደጉ አባቴን የእግዚአብሔርን አንዲቱን የምሕረት ጠብታ አያህልም!!!" በለው። እንዲህ ብለን በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እግዚአብሔር ደስ ይለዋል።ቁጣውን ሁሉ ይተወዋል።ሰው ራሱ ላይ ከልቡ ሲፈርድ እግዚአብሔር ፍርዱን ይተውለታል!!!
“እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፥ ጽድቅንም ይወድዳል፤ ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች።”(መዝ 11፥7) እንዳለ መዝሙረኛው በጽድቅ ራሳችን ላይ ፈርደን፤በልብ ቅንነት ራሳችንን ጻድቅ ለሆነ እግዚአብሔር ስንሰጥ፤እግዚአብሔር ደግሞ የምሕረት ፊቱን ያሳየናል።ይህንንም በልባችን በሚመላብን ፍጹም ሰላምና ደስታ እናውቃለን!!!
"#ሳለ #መድኃኔዓለም" የምወዳት የእናቶቼ ብሂል ናት።እውነትም "#ሳለ #መድኃኔዓለም" #አምላከ #ተክለሃይማኖት!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ኅዳር 13/2017 ዓ.ም