አትሮኖስ
273K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
436 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
​​#ልጩህበት!!


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በጥላሁን

ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭን መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"

ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዋ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰማኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••ኀ
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ከዕለታት_ግማሽ_ቀን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በአሌክስ_አብርሃም

"ልጄን! ልጄን እያለች እናቴ ወደ እኔ
ስትሮጥ ይሰማኛል …ቀለል አለኝ !
።።።።
ለድፍን አንድ ሳምንት ከቤቴ ሳልወጣ አሳለፍኩ፤ ከእሁድ እስከ እሁድ፡፡ ምን እኔ ብቻ፣ ከዚያች ምሽት ጀምሮ እናቴ እንቅልፍ አልነበራትም፣ ለወትሮው ጧት ጧት ሳታዛንፍ የምትስመውን ቤተክርስቲያን ርግፍ አድርጋ ትታ፣ የእኔው ጠባቂ ሆና አብራኝ ታሰረች፡፡ እንኳን ከቤት ርቄ ልሄድ፣ ለሽንት እንኳን ከቤታችን ኋላ ወዳለው መፀዳጃ ቤት ደረስ ብዬ ለመመለስ አታምነኝም፡፡ ተከትላኝ ወጥታ በር ላይ ትቆማለች፡፡ ተጨንቃ ነበር፡፡
እውነት ነበራት ደግሞ፤ ድፍን ከተማው ሌላ ወሬ አልነበረውም፡፡ “የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛው የአቶ ዝናቡ ልጅ እቤታቸው ያስጠጓትን ምስኪን ሕፃን ልጅ ደፈረ…”

እግዚኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦኦ! ስምንተኛው ሺ!”

ጎረቤቱ ከላይ እስከታች በአንድ ጊዜ የነመሐሪን ቤተሰቦች ረጋሚ እና ዘላፊ ሆኖ ነበር፡፡
ይኼ ዘለፋ ታዲያ ባለፍ ገደም ወደኔም እንጥፍጣፊው መድረሱ አልቀረም፡፡ ያስገረመኝ የዚህ የጥላቻ ዘመቻ ዋና አራጋቢዎች ሰፈር ውስጥ ትምህርት እምቢ ያላቸው ልጆች መሆናቸው! እነሱም ብሎ ጎበዝ ተማሪም ይላሉ፡፡ መቼም መሐሪ ሲነሳ “እነሱ” ከተባለ
ያው አንዱ እኔው ነኝ፡፡ እስቲ አሁን ጉብዝናችን ላይ ምን ወስዶ አንጠላጠላቸው? በዚህ ሰበብ ጉብዝናችንን ካዱትም አልካዱትም ትምህርት ሚኒስተር መጽዋች ስለሆነ አይደለም አራት ነጥብ የሰጠን፡፡ ምን ያገናኘዋል? ሲያጨበጭቡልን እየተበሳጩ ነበር እንዴ ሰፈራችንን አስጠራችሁት ያሉት፣ ሰበብ አግኝተው እንደ ኦሪት መስዋዕት ከሰፈር አውጥተው ሊያቃጥሉን ነበር እንዴ? ግን ከተፈጠረው ነገር ይልቅ፣ የተበለጡትን መከረኛ ትምህርት እያነሱ፣ መሐሪንም እኔንም ሲያንቋሽሹ ነበር ውለው የሚያድሩት፡፡
አብሯቸው የኖረ የበታችነት እና የመብለጥ ስሜት፣ ሳሌም የምትባል መርፌ ስትወጋው እንደባሉን እየተነፈሰ ነበር ፡፡

አባባ እንደ ማንኛውም ቀን ፣ምንም እንዳልተፈጠረ፣ በነጠላ እራፊ የተጠመጠመ እግሩን በተደራረበ ትራስ ላይ አሳርፎ፣ (አስር ጊዜ ትራሱን አስተካክልልኝ እያለ)ስለእቁብ
ሲያወራ ይውላል፡፡ ይኼ ነገሩ ትንሽ ቢያሳዝነኝም፣ ከእናቴ ጭንቀት ይልቅ የእርሱ ግድ የለሽነት የተሻለ ያረጋጋኝ ስለነበር፣ ብዙውን ጊዜ የማሳልፈው ከአባባ ጋ በማውራት ነበር፡፡ እንደዛም ሆኖ ግን የሆነ ነገር እንዲለኝ ፈልጌ ነበር፡፡ ቢያንስ አይዞህ እንዲለኝ፡፡
አይዞህ ብቻ፡፡ ምንም ቢያወራ ነገሬ ብዬ ከማልሰማው አባባ፣ አንድ ቃል ናፈቀኝ፡፡
አባትነት ልጅ በመውለድ ብቻ የሚመጣ ነገር እንዳልሆነ የገባኝ ያኔ ነው እየወደድኩት ውስጤ ያዝን ነበር፡፡ ነፍሱ ውስጥ እኔ የለሁም እላለሁ፡፡ ሩቅ
ሐገር ተፈጽሞ በዜና ቢሰማ እንኳን ስሜትን የሚረብሽ ነገር እዚህ አፍንጫው ሥር፣ ያውም ከወንድምም በሚቀርብ የልጁ ጓደኛ ተፈጽሞ ፣ ጎረቤቱ ሁሉ እየዛተና እየፎከረ - “ድሮውንም አንገት
ደፊ” በሚል ገደምዳሞሽ አሽሙር፣ በሌለሁበት እኔንም ጨምሮ እየቀጣኝ ምንም ስሜት ያልሰጠው አባት፣ እንዴት ዓይነት ተፈጥሮ ቢኖረው ነው!? እያልኩ እገረማለሁ፡፡

ለእኔ ብቻ ሳይሆን፣ የእናቴን ጭንቀት ትንሽ እንኳ ቢካፈላት፣ ሌት ተቀን ልጇን ሊነጥቋት እንደከበቧት አራስ ነብር፣ ቁጣና ስጋት ከቧት ስትንቆራጠጥ፡ ኮሽ ባለ ቁጥር ብርክ ሲይዛትና፣ በበር ሽንቁር ወደውጭ እያጨነቆረች ስትመለከት፣ እይዞሽ ቢላት ምናለበት፣ እያልኩ አስባለሁ፡፡ ተኚ እኔ አለሁ ለምን አይላትም? እልናገረውም ግን
አስባለሁ፡፡ ምንም ይሁን አባት፣ ፈርጣማ ክንድ ባይኖረው እንኳ፣ ተስፋና ማጽናናት
እንዴት ይነጥፍበታል፡፡ “እንድ ሰው የልጄን ስም ያነሳና፣ ውርድ ከራሴ፣ እሱ ምን
ያርጋችሁ? እዚህ እንደ እንሽላሊት በየጥጋጥጉ እየሄዳችሁ የምታሽሟጥጡት” ቢል ምን
ይሆናል አንድ ቤት የምንኖር ሳይሆን፣ ታክሲ ፌርማታ ላይ ድንገት ተገናኝተን፣ ታክሲ እስከሚመጣ የምንጠብቅ መንገደኞች የሆንን እስኪመስለኝ ምንም የምንጋራው ስሜት አልነበረም፡፡ ቸልተኛ ነበር፤ እሽ ይሁን፡ ቸልተኝነቱን ትንሽ ወደ ምክር ቢለውጠው እና አይደል፤ አትስማቸው '' ችላ ብሎ ማለፍ ነው" ቢል፡፡

ገና እቤት መዋል በጀመርኩ በሦስተኛው ቀን፡ እናቴን እንዲህ እላት፡፡ “በመንደሩ ያለው ሰው የዝናቡ ልጅ ብቻ ነው እንዴ?…ይውጣና ኮመንደሩ ልጆች ጋር ንፋስ ተቀብሎ ይምጣ፤ እንግዲህ አንዴ የሆነው ሁኗል፡ የፈሰሰ ውሃ እይታፈስ!”፡፡ እንዴ የሆነው ሁኗል ማለት ምን ማለት ነው? እንዳትደግመው እንጂ የሆነው ሆኗል ነበር የሚመስለው አነጋገሩ፡፡ ከዚያ በፊት ችላ ብየው፣ አልያም ሳላስተውለው ቆይቼ የገረመኝ ነገር ደግሞ፣አባቴ መሐሪን በስሙ ጠርቶትም ሆነ ጓደኛህ” ብሎ አያቅም፡፡ “የዝናቡ ልጅ” ነው የሚለው፡፡ ለነገሩ አባባ፣ መሐሪን ብቻ ሳይሆን፣ ሕፃንም ይሁን ወጣት በስም
አይጠራም፡፡ የእከሌ ልጅ ነው የሚለው፡፡ ሴቶችን ሳይቀር “ይች የእከሌ ሚስት” ነው የሚለው፡፡

ይኼው አሁንም “የዝናቡ ልጅ ብቻ ነው ወይ በመንደሩ ያለው? ይለኛል፡፡እና በመንደሩ ማን አለ? …ከመሐሪ ሌላ ማን አለ? …መሐሪ ከሰፈር ልጆች እንዱ አልነበረምኮ መሐሪ ጓደኛ ብቻ አልነበረምኮ ከመኖር ብዛት የራሳችንን ቋንቋ የፈጠርን፣ ሁለት ሰዎች ውስጥ የተቀመጠች አንዲት ውብ ነፍስ የተጋራን ፍጥረቶች ነበርን፡፡ ቃል ሳንተነፍስ
ልባችን ውስጥ ያለውን ሐሳብ በአንድ የዓይን ጥቅሻ የምንካፈል፡፡ ትንሽ ዓለሜ
የቆመችው፣ ሁለት ምሰሶዎች ላይ ነበር፡፡ አንዱ እኔ ራሴ፣ አንዱ መሐሪ! ግማሽ እኔ እስር ቤት ውስጥ ነኝ ሚዛኗን ስታ እየተንገዳገደች ያለች ሚጢጢ ዓለሜን፣ ወደፊት መራመዱ ቢቀር፣ ቀጥ ብላ እንድትቆም እየታገልኩ ነበር፡፡ ለድጋፍ እጁን የሚሰጥ ሰው እንጂ፣ ግዴለም በአንድ እግርህ ውጣና፣ ሌላ እግር ፈልግ የሚል ሰው አልነበረም ፍላጎቴ! “ከሰፈር ልጆች ጋር ነፋስ ተቀበል” ይለኛል፡፡ እንኳን አብሬው ነፋስ የምቀበለው የሰፈር ልጅ፣ በመንደሩ ውስጥ ነፋስ አለ ወይ?… መንደሩስ ራሱ አለወይ … እቤቴ ቁጭ
ያልኩት (ምን ቁጭ ያልኩት የተደበኩት) እንደ ሕፃን ልጅ የራሴን ዓይን ስጨፍን
ከዓለም ሁሉ የተደበቅሁ መስሎ እየተሰማኝ፣ ለአፍታም ቢሆን እፎይታ ስለሚሰማኝ ነበር፡፡ በሆነው ሁሉ ከማፈሬ ብዛት የሰው ዓይን ፈርቼ ነበር፡፡
መሐሪ ሁለት ቀን ፖሊስ ጣቢያ ቆይቶ በሦስተኛው ቀን ፍርድ ቤት ቀረበ ተባለ፡፡ የዚያኑ ቀን ከሰዓት በኋላ፣ ወደ ትልቁ ማረሚያ ቤት እንደተወሰደ ሰማሁ፡፡ ይኼን ሲነግሩኝ፣ ያ አሮጌ የብረት በር እየተንሳጠጠ ከኋለው ሲከረቸምበት ታየኝ፡፡ ውስጤ ሂድ ሂድ ይለኛል፡፡ከስንት ዓመታት በፊት ያየሁት ማረሚያ ቤት ሲታወሰኝ፣ዘገነነኝ፡፡ የማቅለሽለሽ
ስሜትም ተሰማኝ፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ፣ ዝም ብሎ የማቅለሽለሽ ስሜት ቶሎ ቶሎ
ይሰማኛል፡፡ሳምንቱን ሙሉ እንደ ነፍሰጡር ምግብ ሲሸተኝ፣ ጧት ስነሳ ያቅለሸልሽኝ ነበር፡፡

ግንኮ እስከ ዛሬ ብዙ ነገር ይስተካከል ይሆናል” ብዬ እራሴን ለማጽናናት ሞከርኩ፡፡ለምሳሌ ማረሚያ ቤቱ ውስጥ ዘመናዊ የመዋኛ ገንዳ ተሠርቶ ሊሆን ይችላል (መሐሪ ዋኝቶ አያውቅም እንጂ ዋና ይወዳል፡፡ ስናድግ እቤቱ የመዋኛ ገንዳ ሊያስገባ ሐሳብ ነበረው) ምናልባት ምሳቸው በባልዲ የተቀዳ ወጥ ሳይሆን፣ ነጫጭ ልብስ በለበሱ ጠረጴዛዎች ላይ፣ በቆንጆ አስተናጋጆች በሸክላ ሰሀን የሚቀርብ ብዙ ዓይነት ምግብ ሊሆን ይችላል፡፡ በቅመም ያበደ ሻይም ከምሳ በኋላ ይቀርብላቸው ይሆናል። (መሐሪ
ከምሳ በኋላ እንደዚያ ዓይነት ሻይ ይወዳል) ከዚህ ሁሉ
#ለኀጥአን_የመጣ

#ክፍል_አስራ_ሶስት

#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ

#በኢስማኤል_ቤህ

#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው


መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን
ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን ሰላምታ ከተሰጣጣን በኋላ ጁማህን መፈለግ
ጀመርን። ፊቱን ወደ ጫካው ያዞረ ጡብ ቤት ደጃፍ ላይ ዥዋዥዌ ላይ ተቀምጦ ነበር። ከጎኑ መሳሪያ ነበር። ቀስ ብለን ወደ እሱ ስንጠጋ ፊቱን አዞሮ አየን።

ከባድ መሳሪያ ይዘህ ነው ምትዞረው ማለት ነው?” ብሎ አል ሃጂ ቀለደ።

“እንግዲህ ምን ታረገዋለህ! ከ AK ከፍ እያልኩ ነው” ብሎ መለሰ።ሁላችንም ሳቅን።

ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እንደምንመለስ ነግረነው ጥይት እና ምግብ ልንጭን ወደ መጋዝን ሄድን።መጋዝን እያለን አዛዣችን፥ መቶ አለቃ “ዛሬን ከዚህ እደሩ፤ እራት ተዘጋጅቷል” እንዳለ ነገረን፡፡ አልራበኝም፡ ስለዚህ ኬን እና አል ሃጂ ወደ እራት
ሲሄድ እኔ ተለይቼ ወደ ጁማህ ተመልሼ ሄድኩ። ማውራት ከመጀመሩ በፊት ለደቂቃዎች ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡

ነገ በጥዋት ለውጊያ ስለምወጣ ከመሄዳችሁ በፊት አላይህም” ብሎ ዝም አለ እና መሳሪያውን እየነካካ ቀጠለ:
የዚህን መሳሪያ ባለቤት ገደልኩት።
ብዙዎቻችንን ከገደለ በኋላ ነበር የደረስኩበት። ከዛ በኋላ ነበር እኔ የያዝኩት ”ብሎ ፈገግ አለ፡፡ እጃችንን አጋጨንና ሳቅን።ወዲያውኑ እንድንሰበሰብ ተጠራን:: ተሰባስቦ መጫወቻ እና
የአዛዦችን መተዋወቂያ ማህበራዊ ፕሮግራም ነበር። ጁማህ መሳሪያውን በአንድ እጁ ከያዘ በኋላ በሌላ እጁ ጫንቃየ ላይ አድርጎ አቅፎኝ ወደ መሰብሰቢያው ሜዳ ሄድን።ኬን እና አል
ሃጂ ከዛው እያጨሱ ነበሩ። መቶ አለቃም በቦታው ነበር። ትንሽ ፈንጠዝያ ነበር። የመቶ አለቃ ጓደኞች አብዛኞቹ ማለትም ሃምሳ አለቃ ማንሳራይ እና አስር አለቃ ጋዳፊ ሙተዋል። እሱ እንዴት
እንደተረፈ አይታወቅም። በተዕምር ምኑም ሳይነካ የለአንዳች ጠባሳ ተርፎ ሌሎች ሃይለኛ እና ታዛዥ ጓዶችን በሞቱ ጓደኞቹ ምትክ ለማፍራት በቅቷል።መቶ አለቃ ጋር ስለ ሼክስፔየር ማውራት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን እሱ በማስተባበር ፤ ሰላም በመስጠት ተጠምዶ ነበር። በመጨረሻ እኔ ፊት ለ ፊት ሲደርስ
እጄን ጥብቅ አርጎ ያዘና “ማክቤዝ አይበገርም፧ ታላቁ የብሪያም ጫካ ዶንከን ኮረብታ እስኪደርስ ድረስ ማክቤዝ እጅ አይሰጥም አለ።

ጮክ ብሎ ”ልለያችሁ ነው ጓዶች” አለ። እጅ ከነሳን በኋላ እጁን እያውለለበ ሄደ። እኛም መሳሪያችን ከፍ አድርገን በጩኸት
ሰላምታችን ገለጸን። መቶ አለቃ ከሄደ በኋላ የሴራሊዮንን ብሄራዊ መዝሙር መዘመር ጀመርን። “ከፍ አድርገን
እናከብርሻለን፤ የነጻ ህዝቦች ሃገር፤ ጥልቅ ነው ለአንቺ ያለን ፍቅር” ለሊቱን ሙሉ ስንጫወት ስናወራ አሳለፍን።
ከመንጋቱ በፊት ጁማህ እና የተወሰኑ ወታደሮች ለውጊያ ሄዱ። አል ሃጂ፣ ኬን እና እኔ በሚቀጥለው ጥየቃ ብዙ
እንደምንጫወት ቃል ገብተን ተሰናበትነው:: ጁማህ ፈገግታ ካሳየን በኋላ መሳሪያውን ጠበቅ አድርጎ ከያዘ በኋላ ወደ ጫካው ገባ፡፡

ከትንሽ ስዓታት በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ወደ መንደር መጣ፡፡ ዩኒሴፍ UNICEF የሚል ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ የለበሱ
አራት ሰዎች ከመኪናው ወርደው ወደ እኛ መጡ። አንድ ነጭ እና ቆዳዋ ነጣ ያለ ምንአልባት የሊባኖስ ሰው እና ሌሎቹ የሃገሩ ሰዎች ሴራሊዎናውያን ናቸው:: ጦርነቱን ያዩ አይመስሉም የተመቻቸው ነበሩ። ወደ መቶ አለቃ ተልከው የመጡ ይመስላሉ። እሱም ሲጠብቃቸው ነበር፡፡ ቤት ደጃፍ ተቀምጠው ሲያወሩ ከማንጎ ዛፍ ስር ተቀምጠን መሳሪያችንን
እየወለወልን እናያቸው ነበር። በኋላ መቶ አለቃ ከሁለቱ የውጭ ሃገር ሰዎች ጋር እጅ ተጨባበጠ፡፡ ጠባቂው ወደ እኛ መጣ እና እንድንሰለፍ ነገረን። ሰፈሩን እየዞረ ከ “ መቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው!” ትዕዛዝ መቀበል እና የታዘዝ ነውን መፈፀም ለምደናል። ወደ ጎን መስመር ሰርተን መጠበቅ ጀመርን።

መቶ አለቃ ከፊታችን ቁሞ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠን፡፡ ሌላ ግዳጅ እየጠበቅን ነበር፡፡ “አሳርፍ” ብሎ ቀስ ብሎ መራመድ
መቃኘት ጀመረ፡፡ እንግዶቹ ከጀርባ ነበሩ።
“ስጠቁም ወደ ጠባቂየ በመሄድ ትሰለፋላችሁ ገብቷችሃል።”ሲል “አዎ! አለቃ” ብለን ጮህን፡፡

“አንተ፣ አንተ.....” መቶ አለቃ እየመረጠ እስከ ሰልፉ መጨረሻ ደረሰ፡፡ መቶ አለቃ እኔን ሲመርጠኝ አትኩሬ ተመለከትኩት።
እሱ ግን አላየኝም:: አል ሃጂም ተመረጠ። ኬን ግን ትልቅ ስለሆነ አልተመረጠም:: “መሳሪያችሁን የጥይት ካዝና አወላልቃችሁ መሬት ላይ አስቀምጡ” የሚል ትዕዛዝ ከመቶ አለቃ ሰጠ፡፡ መሳሪያችንን አወላልቀን መሬት ላይ አስቀመጥን።መቶ አለቃን ተከትለን እንግዶች ወደ የመጡበት ገልባጭ መኪና ሄድን። መቶ አለቃ ፊቱን ወደ እኛ ሲያዞር ቆምን “ ጎበዝ ጀግና
ወታደር ነበራችሁ! ታውቃላችሁ የዚህ ወንድማማችነት እና ሃገርን የማዳን ጥሪ አካል እንደነበራችሁ። ከእናንተ ጋር ሃገሬን
በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል። ኮርቼባችዋለሁ። አሁን ስራችሁ
እዚህ ጋ ያበቃል። ልለቃችሁ ይገባል። እነዚህ ሰዎች ትምህርት ቤት ያስገቧችኋል፤ ሌላ መልካም ህይወት እንዲኖሩዋችሁ ይረድዋችኋል።” ይሄን ብቻ ነበር ተናግሮ ትቶን ሄደ:: ቀጥሎ
ፍተሻ ነበር። ሰንጢ እና ቦምብ ይዤ ስለነበር መፈተሽ አልፈለኩም፡ ፈታሹን ብትነካኝ እገልሃለሁ ብየ ዛትኩበት። ከእኔ
ጎን ወደ አለው ቀጠለ።

ምን እየሆነ እንዳለ አልገባኝም? መቶ አለቃ ለእነዚህ ሰዎች ለምን አሳልፎ ሊሰጠን እንደወሰነ አልገባኝም። ጦርነቱ እስኪበቃ ድረስ የምንቀጥል መስሎን ነበር፡፡ ግን ያለምንም ማብራሪያ
ተወሰድን፡፡

መኪና ውስጥ የደንብ ልብሳቸው ንጹህ እና መሳሪያቸው አዲስ የሆነ ሶስት ፖሊሶች ነበሩ። ፖሊሶቹ ከገልባጩ ወርደው እኛ እንድንወጣ ጠቆሙን። ወጥተን ሁለት አግድም ወንበሮች
ላይ ፊት ለ ፊት ተቀመጥን። ፖሊሶች መውረጃው ላይ ተቀመጥን።

አል ሃጂ እና እኔ በመገረም በብስጭት ተያየን። የት እንደሚወስዱን እንኳ አናውቅም። ለስዓታት ተጓዝን። ያለምንም ስራ ቁጭ ብሎ መጓዙ አድካሚም
አሰልቺም ነበር፡፡ መኪናውን ጠልፎ ወደ ባውያ ለመመለስ አሰብኩ። መሳሪያውን ለመንጠቅ ስዘጋጅ መኪናው ለፍተሻ
ፍጥነቱን ቀንሶ ፖሊሶቹ ወረዱ።
መቀመጥ ስላልቻልኩ በጉዞ በሙሉ እረፍት አልነበረኝም ያቁነጠንጠኝ ነበር። የፍተሻ ጣቢያዎች ስንደርስ ትንሽ ፈታ እል ነበር። በመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያ ያገኘናቸው ወታደሮች የሚያምር ደንብ ልብስ የለበሱ መሳርያቸው አዲስ ነበር።

በኮሮኮንች መንገድ የመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያውን አልፈን እንደሄድን የተጨናነቀ የአስፓልት መንገድ ደረስን። ዙሪያውን
መኪኖች በተለያየ አቅጣጫ ሲጓዙ አየሁ፡፡ በህይወቴ የዚህን ያህል ብዙ መኪኖች አይቼ አላውቅም፡፡ መርሰዲሶች፣ቶዮታዎች፣ማዝዳዎች፣ቼርቮያለ ትዕግስት ሲያጮሁ ሙዚቃ ሲያጫውቱ ነበር፡፡ የት እንደምንሄድ አሁንም አላውቅም ነገር ግን Freetown ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ እንዳለን
አውቂያለሁ።ለምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም፡፡

ውጩ እየጨለመ ነው። መኪናችን በዝግታ ወደ ተጨናነቀው መንገድ ሲገባ የመንገድ መብራቶች ተራ በተራ
እንደፍንጣቂ ነገር ቦግ ቦግ እያሉ መብራት ጀመሩ። የሱቆች እና
የመጠጥ ቤት መብራቶች ሳይቆጠር ብዙ መንገድ መብራቶች ከተማዋን አንቆጥቁጠዋታል። የከተማዋ ፎቆቹም በብዙ ብርሃን የተንቆጠቆጡ ናቸው። ለተወሰኑ ደቂቃዎች በፍጥነት
#ሰመመን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...“ይቺ በመቀጨጭ ላይ ያለችዋ ” አሉ ዮናታን' ወደ ቆርቆሮው ውስጥ በጣታቸው እያመለከቱ።

“ እም ፡ አዎ ከእንግዲህ የምታድግ አትመስልም ”አሉ ዶክተር አጥናፉ ፥ ብዙም ባልተደነቀ ስሜት ።

“ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፡ ዐይናቸውን ወደ እስጉብኝው እያሸጋገሩ ።

“ አካባቢው ኣልተስማማት ይሆናላ ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ ፡ በቀልድ ዐይነት ! “ ወይም ደግሞ ፍሬዋ ከጓደኞቿ ተለይታ በተለየ ዐፈር ውስጥ መብቀል ፈልጋ ይሆናል ። ”

ከት ብሎም ባይስቅ እስጐብኝው ፈገግ አለ ። ዮናታን ግን የተቋጠረው ግንባራቸው አልተፈታም " ይብሱን ነገሩን
አጠንክረው
“ የአካባቢም ተጽፏኖ ሆና የዐፈሩ አለመማማት ፥ወይም ሌላ ችግር ፡ የስንዴዋ መቀጨጭ ከአያያዝ ግድየለሽ
ነት የመጣ ነው ። ገና ከእንጭጭነት ችግሯን አስተውሉ አካባቢዋን ወይም አፈሯን መለወጥ ቢቻል ኖሮ ለዚህ አት
ደርስም ነበር ። ግን አንድ ነች ። አንድ ነገር አንድ ነውና አብዛኛውን ጊዜ አናስብበትም ። አናስተውሰውም ። ጣሳው ሙሉ ተክል ሊበላሽ ቢሆን ኖሮ ግን ወዲያው መፍትሔ በተ ፈለገለት ነበር

አስጐብኝው በድንጋጤ ክው ብሎ ቀረ አምርረዋል ወይሰ ይቀልዳሉ ? ” አለ በልቡ እሱም ። አማካሪው ዶክተር ኤጥናፉ ቸል ያሉትን ነገር ዮናታን አምርረው መያዛቸው ምክንያቱ አልገባህ አለው ። “ ምነው ባልጋበዝኳችው ! ” አለ በልቡ ፡ አነጋገራቸው ዶክተር አጥናፉን
ይላውጥብኛል ብሎ ስለፈራ ዮናታንን በጥላቻ እያያቸው

“ ይህ እኮ አብዛኛውን ጊዜ ሊደርስ የሚችል አጋጣሚ ነው ። ደግሞስ የአንዱ መቀጨጭ ምን ያህል ይጎዳል ብለህ
ነው ? የዐፈሩ ተጽዕኖ በአብዛኛው ስንዴ ዕድገት ሲለካ ይችላል ዶክተር ፡ አሁንም ለነጎሩ ክብዶት ሳይሰጠት ።

“ ይጐዳል እንጂ እንዴት አይጐዳም ?” አሉ ዮናታን አምርረው ። “ የቆርቆሮው ተክል እኮ ስምንት የምታሰኘው
ይህቺ አንዷ ስትጨርስ ነበር ስትጐድል ግን ሰባት ታረገዋለች።አንድ ሳንቲም “ ዋጋ የለውም” እንላለን ። ግን “ ዋጋ
እንዳልው የምንረዳው አራት ሳንቲም ይዘን ስንቀር ነው ”

አስጐብኝው የባሰውን በጥላቻ ገላመጣቸው ። እሳቸው ግን ልብ አላሉትም ። እሱን መጉዳታቸውም አልታወቃችውም ። ዶክተር አጥናፉ ራሳቸው፣ “ሰውዬው አበደ እንዴ?”
በማለት ዐይነት በሆዳቸው እየሣቁ ፥ ምንም ሊጠይቁ ወይም ሊናገሩ ስላልቻሉ ዝም አሉ ።

ከጥቂት ዝምታ በኋላ ዮናታን ልምጭጭ ፈገግታ እያሳዩ' በምጸታዊ አነጋገር “ አየህ የአቤልም ነገር እንዲሁ ነው ” አሏቸው ።

ዶክተር አጥናፉ የዮናታን ውስጣዊ ስሜት እንዲህ የተለዋወጠበት ምክንያት ያው ገባቸው ። ስለ አቤል ጉዳይ ደጋግመው አነጋግረዋቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ለጉዳዩ ብዙም ክብደት ወይም አትኩሮት ባለመስጠት ቸል ብለውት ስለቆዩ
አሁን ጥያቄም ይሁን መልስ ማንሣት አልፈለጉም። ሐሳባቸውን ሁሉ ወደ ተክሉ በመሰብሰብ ዐይነት ከአስጐብኝው
ጋር ሐሳብ በመለዋወጥ ዮናታን የተነሡበትን ሐሳብ ለማዘናጋት ሞከሩ ። ይሁን እንጂ ፥ ዮናታን ውስጥ የሚንቦገቦገው ሐሳብ በቀላሉ የሚበርድ አልነበረም። ጉብኝቱን ጨርሰው
ከተክሉ ቤት ሲወጡ እንደ ገና አነሡባቸው ።

“ ሁላችሁም የዚህን ልጅ ጉዳይ ቸል ማለታችሁ ነው ? ያቤልን?እንዴትነው? አሁንም አልተሻለው?” አሉ ዶክተር
አጥናፉ ሸሽተው የማያመልጡት ነገር መሆኑን ገምተው ።

ይሻለዋል ? ጉንፋን ” ኮ አይደለም ያመመው ።ይህኛው አነጋገራቸው ቁጣ ብቻ ሳይሆን ተስፋ መቁረጥም
ነበረበት ።

የዮናታን አነጋገር ዶክተር አጥናፉን አላስቆጣቸውም ።የቅርብ ጓደኝነት ስላላቸው አንዳቸው የአንዳቸውን ጸባይ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡ዮናታን ከውስጥ ሥቀው ከላይ ጥርሳቸውን ማሳየት አይችሉም ። የተማረሩበትን ወይም የበሽቁበትን ነገር ማንም ፊት ይሁን ከማንም ጋር ፊትለፊት በቁጣ ተናግረው ነው የሚወጡት ። ከዚያ ንዴቱ ቢበርድላቸው ያው ሰው አክባሪነታችው ፍቅር የተሞላበት ሰላምታችሙ
ዮናታንነታቸው ይመለሳል ። ነገር ግን የዚህ ልጅጉዳይ ይህን ያህል ለምን እንዳንገበገባቸው ዶክተር አጥናፉ ጥርት ብሎ ሊታያቸው አልቻለም ።

“ ችግሩ ኮ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፥ የዮናታንን ቁጣ ማስታገሥ በሚችል ለዘብ ያለ አነጋገር ። “ ችግሩ የሁሉም አለመተባበር ነው ። ከአሁን በፊት በዩኒቨርስቲው ውስጥ እንዲህ ዐይነት ጉዳይ ትልቅ አትኩሮት ተሰጥቶት
ስላልተሠራ አሁንም ...

ዮናታን አላስጨረሳቸውም ።

“ እኔም እኮ የምለው ይህንኑ ነው ። ለምን አትኩሮት አይሰጠውም ? በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ካሉት ችግሮች አንዱ
አይደለም ወይ? አየህ ! ፍቅር ሲሠምር ፥ ሲገኝ ሲያብብ ደስታ ፍሥሐ ነው ። ከመገኘቱ በፊት ወይም ተግኝቶ ሲጠፋ ኃይለኛ ጥማት ፡ ሥቃይ ሕመም ነው ፥ ” አሉና፡ ነገሩን ከውሉጋር እንደማያያዝ ትንሽ ካሰቡ በኋላ ፥ “ አዎ ! እና ፥ ምንም
ይሁን ምን የ ግለሰብን ከዓላማው ወይም ከግቡ የሚያዘናጋ ወይም ራሱን የሚያስጠላ ሁኔታ እስከሆነ ድረስ መድኃኒቱ መፈለግ አለበት አሁን አቤል በዚህ ሁኔታ ተጨናግፎ ትምህርቱን ቢያቋርጥ ወይም ተደባብሶ ቢመረቅ ፡ ሁለተኛ ወደ ትምህርትና ምርምር ዓለም ፊቱን እንደማይመልስ አታውቅም ? ”

“ እሱ እንኳን በጤናቸው የሚመረቁትም የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ጸባይ ነው ። ሺ አስመርቀናል ፤ ነገር ግን
ምንም ተአምር የሠራ አላየንም አሉ ዶክተር አጥናፉ በንቀትና ተስፋ በቆረጠ ስሜት ።

ይህ የሚሆነው ለምን ይመስልሃል ? ! በእኔ ግምት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቶቻቸውን በፍቅር እንዲጀምሩ
ስለማናደርጋቸው ነው ።ሳያስቡት ዶክተር አጥናፉ ቢሮ ስለ ደረሱ ። በሩን ለመ
ክፈት ቁልፉን እየጠመዘዙ አሁንም በተሰላቸና ነገሩን ቶሎ ለመቁረጥ በዳዳ ስሜት • “ ብቻ ሁሉም ነገሩን እንዳንተ
ቢያስብበት ምናልባት ውጤት ያገኝ ይሆናል ። ግን እንዳየሁት ይህን ጉዳይ ብሎ ኮሚቴ ላይ አቅርቦ መፍትሔ ለመ
ፈለግ የሚሻ ሰው እንጂ ”

“ ይህ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፥ ተከትለዋቸው ወደ ቢሮ ውስጥ እየገቡ ፤ ይህ ራሱ ምሁርነታችን የሚያስከትልብን በሽታ ራሳችንን በጣም ከፍ አድርገን ስለምንግምት ከኛ በኋላ ሰው የሚፈጠር አይመስለንም ። ዐይናችንን ገልጠን ከተማሪዎቻችን መሐል ታላላቅ ሰዎች ሊበቅሉ እንደሚችሉ ማየትና መገመት አለብን ።
ይህ ስሜት ሲኖረን ብቻ ነው ተማሪዎቻችን እንቅፋት እንዳይመታቸው ልንጠነቀቅላቸው የምንችለው ”

“ ስደበና! ” አሉና ዶክተር አጥናፉ በቀልድ ፡ “ ለማንኛውም እስኪ ቁጭ በል” ሲሉ ዮናታንን ጋበዟቸው ።

“ አልቀመጥም ” አሉ ዮናታን ሰዓታቸውን እየተመለከቱ። “ ኦ! እንዲያውም ሰዓት አሳለፍን ። በአሥር ሰዓት አንድ ተማሪ ቀጥሬ ነበር።

“ እሺ እስቲ እንግዲህ በሚቻለን መንገድ እንታግሳለና ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ " ጉዳዩ ከውስጥ ባይፈነቅላቸውም ዮናታንን ለማስደስት ያህል "

“ በውነት እንዲያው በሚቻለን መንገድ ይህንን ልጅ መርዳት አለብን ። እባክህ ቸል አትበል ” አሉ ዮናታንም ረጋ ባለ አንደበትና ረዳት በሚፈልግ ስሜት ወደ
ከዚያ ፥
ወዲያው ወጥተው በመኪናቸው ወደ ስድስት ኪሎ በረሩ ። ከቢሮአቸው ሲደርሱ እስክንድር መዝጊያን
ተደግፎ ቆሞ አገኙት።

““ ሶሪ ዘግየሁብህ አይደለም ? ” አሉት በሩን ለመክፈት እየተቻኮሉ ። ዐሥር ደቂቃ አሳልፈውበት ነበር ።ጠዋት ገለጻ ክፍላቸው ውስጥ ክፍለ ጊዜኣቸውን ጨርሰው ሲወጡ ነበር በዚህ ሰዓት እንዲያገኛቸው የቀጠሩት ። የፈለጉት ለአቤል ጉዳይ መሆኑን ፈጽሞ አልተጠራ
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....“ወ/ሮ ሮበርትስ ባለቤትሽ ከሞተ በኋላ ለምን ያህል ጊዜ ነው ሥራ ፈተሽ የተቀመጥሽው?” ብሎ ጠየቃት መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን፡፡

ኒኪ በመመርመሪያ ክፍሉ ውስጥ ባለው ጠረጴዛ ሥር የሚገኘው መዳፏን በጥፍሯ እየወጋች ከአንድ እስከ አሥር ቆጥራ ጨረሰች፡፡በውስጧም ይሄ ሰው እንዲያናድደኝ እና ስሜታዊ ሆኜ እንድናገር እንዲያደርግ ልፈቅድለት አይገባም፡፡ በቃ የንዴት ስሜቴን እንዲያነሳሳብኝ በፍፁም ልፈቅድላት አይገባም፡፡ በፍፁም እሱ የሚፈልገውን ነገር ልሰጠው አይገባኝም አለች በውስጧ፡፡
“ይቅርታ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን ዶ/ር ሮበርትስ ነኝ” ብላ ድምጿን ለስለስ በማድረግ ስሟን ከሙያ ማዕረጓ ጋር እንዳልጠራት እና አስተካክሎ ስሟን እንዲጠራት ለማሳሰብ ብላ “ይህንን የዶር ማዕረጌን አስተካክለህ እና አስታውሰህ ለመጥራት ያስቸገረህ ይመስለኛል፡፡ ሁሌ እንደዚህ አይነት የማስታወስ ችግር አለብህ? ወይንስ ከዕድሜ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የመርሳት ችግር ነው ያለብህ?” ብላ ጠየቀችው፡፡

የዶ/ር ኒኪ ሮበርትስን መልስ የሰማው ጆንሰን ፊት በንዴት በጣም ከመቅላቱም በላይ መንጋጋውንም በንዴት ነክሶ ዶክተሯን ያያት ጀመር: አብሮት ያለው ባልደረባው ጉድማንም በኒኪ መልስ እና በጆንሰን ሁኔታ የመጣበትን ሳቅ
ውጦ አስቀረው። ዶ/ር ሮበርትስ ጥያቄዎችን የምትመልስለት ስሜቷን ተቆጣጥራ ሲሆን ጆንሰን ደግሞ በተቃራኒው ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ በንዴት ስሜት ነበር የሚመለከታት፡፡

“እኔ ምንም አይነት የማስታወስ ችግር ኖሮብኝ አያውቅም ሴትዮ ያንቺን ሙያ የማሞካሽበት የማዕረግ ስምሽ ለእኔ ምኔም አይደለም። በዚያ ላይ ደግሞ ሁለታችንም ትክክለኛ ዶክተር እንዳልሆንሽ በደንብ እናውቃለን።
አላት በንዴት እየጦፈ፡፡

ሚክ በንዴት ሊፈነዳ የደረሰ በጣም የበሰለ ቋሊማ ሆኗል። ባልደረባው
ሚክ ጆንሰን ከሴቶች ጋር ያለው ግንኙነት ጥሩ እንዳልሆነ ባልደረባውዐጉድማን ያውቃል። በተለይ ደግሞ እሱ በማያውቀው አንድ ምክንያት በዚህች
ሴት ላይ ያለው ጥላቻ ሥር የሰደደ መሆኑን ጉድማን ለመታዘብ ችሏል።
ይሄ ግን ለምን እንደሆነ ሊገባው አልቻለም:: በእሱ አመለካከት ዶ/ር
ሮበርትስ ዛሬ ይበልጥ ውብ ሆና ነው የመጣችው። የእርሳስ ቀለም ያለው
ጉርድ ቀሚስ እና ከቀሚሷ ጋር የሚስማማ የሀር ሸሚዝም አድርጋለች።
ሰውነቷ ጥብቅ ያለ መሆኑንም በአይኑ እያየው ነው። በዚያ ላይ ደግሞ
እርጋታዋ እና ሁሉንም ስሜቶቿን መቆጣጠር መቻሏ ይበልጥ የምትስብ
አድርጓታል፡፡ በሉው ጉድማን አይን ደግሞ እንደዚህ ራሳቸውን እና ስሜታቸውን የሚገዙ ሰዎች ይበልጥ አይንን የሚስቡ ቆንጆ ሴቶች እንደሆኑ ይገምታል፡፡

“ጥያቄውን ብቻ መልሺ! ለምን ያህል ጊዜ ነበር ሥራ ፈትተሽ የተቀመጥሽው?” ብሎ ጆን በቁጣ ድምፅ ጠየቃት፡፡

“ወደ ስድስት ሳምንት ገደማ ያህል።” ብላ ኒኪ መለሰችላት፡፡

“ረጅም ጊዜ ይመስላል?”

“ብለህ ነው?” ብላ ኒኪ በአጭር ሀሳቡን ቆረጠችበት፡፡

“አዎ ረዥም ጊዜ ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ለመኖር ሁላችንም መሥራት ይጠበቅብናል። እኛ እንደ አንቺ አይደለንም፤ ያለ ሥራ ለብዙ ጊዜ መቆየት
አንችልም እና ጉራሽን ባትቸረችሪብን ደስ ይለናል ወ/ሮ ሮበርትስ። ምናልባት የሞተው ባልሽ ብዙ ሀብቶችን ስለተወልሽ አሁን ላይ ሀብታም ሴት ለመሆን ችለሻል” አላት፡፡

ኒኪም መርማሪው ስለ እሷ ሀብታምነት እንደዚህ መዘርዘሩ እና የነገሩ አካሄድ ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም::

“ዶውግም በህይወት እያለ ቢሆን እኮ እኔ የገንዘብ ችግር የሌለብኝ ሰው ነበርኩኝ አቶ ጆንሰን። ስለዚህም የእሱ መሞት በእኔ ገቢ ላይ ምንም አይነት ለውጥ አያመጣብኝም።” አለች።

“ህምም” ብሎ ጆንሰን አጉረመረመ እና በመቀጠልም “ከመቼ ጀምሮ ነው
ትሬይ ትሬቮን አንቺ ጋር ተቀጥሮ መስራት የጀመረው?” ብሎም ጠየቃት።
ኒኪም በሀዘን ስሜት ውስጥ ሆና በረዥሙ ተነፈሰች። የትሬይን መሞት
እስከ አሁን ድረስ አምና መቀበል አልቻለችም:: የእሱን ህይወት አስመልክቶ
ለዚህ ደነዝ ፖሊስ ምንም አይነት ነገር መናገር አትፈልግም።

“እኔ እንጃ መቼ እንደሆነ በእርግጠኝነት አላስታውስም።”

“እሺ ወደ ሥራ ከተመለስሽ በኋላ ነው ወይንስ ባልሽ በአደጋ ከሞተ
በኋላ?”

“እሱ ከሞተ በኋላ ነው” ብላ ኒኪ መለሰችለት እና ወደ ጉድማንም
በመዞር “እነዚህ ጥያቄዎች ከግድያው ጋር ያላቸውን ግንኙነት አልተረዳሁም፡፡ ከዚህ ይልቅ ግን ከዚህ ክፍል በመውጣት ሊዛ እና ትሬይን ማን እንደገደላቸው ማወቅ እና መያዝ አይገባችሁም? ማለቴ ከእኔ ጋር የሚሰሩ ሰዎችን የቅጥር ጊዜ መጠየቁ መፍትሄ አለው ብላችሁ
ታስባላችሁ?”

አሁንም እኮ እያደረግን ያለነው አንቺ የምትናገሪውን ነገር ነው?” ብሎ
ጆንሰን በቁጣ ድምፅ በመቀጠልም “በሁለቱ ግድያዎች መካከል ያሉትን
ግንኙነቶች ለማየት ሞክረን ነበር። ገምቺ እስቲ... ሁለቱ ሟቾች በጋራ የሚያውቁት አንድ ሰው አለ፡፡” ብሎ ወንበሩ ላይ ከተለጠጠ በኋላም በጠቋሚ
ጣቱ ወደ ኒኪ ቀስሮ “አንቺ ነሽ ዶክተር ሮበርትስ?” አላት።
“እኔ ሊዛን እና ትሬይን እንደገደልኳቸው ታስባለችሁ?” ብላም ሁለቱን መርማሪ ፖሊሶች ጠየቀቻቸው፡፡ ጥያቄዋን ስታቀርብ ፊቷን ወደ ጆንሰን
አዙራ ስለነበር የጠየቀችው ጆንሰን መልስ ለመስጠት ወፍራም ከንፈሩን
ከፍቶ ሊመልስ ሲል ጉድማን ከወንበሩ ላይ ዘሎ ተነሳ እና “ እንደዛ ማለታችን አይደለም” ብሎ በማስከተል “አንቺ ሁለቱም ሟቾች የሚያውቁሽ ሰው ነሽ፡፡ ስለዚህ ምናልባት ነፍሰ ገዳዩ ከአንቺ ጋር የሆነ ግንኙነት ሊኖረው ይችላል ብለን እንድናስብ እንገደዳለን። አለ አይደል የቀድሞ ታካሚሽ ሊሆን ይችላል። የአሁን ላይ ታካሚሽም ሊሆን ይችላል፤ በአንቺ የሥራ ሁኔታ ደግሞ በጣም የተረበሹ ሰዎች ገጥመውሽ ሊሆን ይችላል። ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ በአንቺ እና በአንቺ ዙሪያ ከሚገኙ ሰዎች ጋር የከረረ ግንኙነት ሊኖረው ይችላል። ምናልባትም ይሄ አደገኛ ግለሰብ ሊሆን ይችላል ግድያውን የፈፀመው ብለን እናስባለን።”

ኒኪ ጉድማን የነገራትን ነገር አሰላሰለች። ግን በአዕምሮዋ ውስጥ ይህንን
ሊያደርግ የሚችል ሰው ሊመጣላት አልቻለም። በእሷ ሥራ ላይ እንደሚገኙት ባልደረቦቿ እሷ አንድም ቀን ቢሆን በታካሚዎቿ ጥቃት ደርሶባት አያውቅም። አንዳቸውም ቢሆኑ ከእሷ ጋር ያልተገቡ የፍቅር ስሜቶችን አስተናግደው አያውቁም። እርግጥ ነው አንድ ታካሚ ከቴራፒስቱ ጋር የቀቢፀ ተስፋ እሳቤ ሊኖረው ይችላል። ግን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ ሁለት ሰዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሊግድላቸው አይችልም።

“ስለዚህ የበፊት እና የአሁን ታካሚዎችሽ የግለሰብ መዝገቦችን ማየት እንፈልጋለን፡፡” ብሎ አስረዳት፡፡

“መልካም” ብላ ኒኪ በሀሳብ ጭልጥ ብላ ጠፋች።

“የሁሉንም ታካሚዎችን መዝገብ ነው የምንፈልገው።” ብሎ ጆንስን ጮህባት
እና “ግን ምንም አይነት አርትዖት ሳታደርጊባቸው እና ምንም አይነት የሀኪም እና ታካሚ ሚስጥር መጠበቅ የሚባል ነገርን ሳታደርጊ ነው” አላት ጆንሰን፡፡ “ምናልባት እኮ ነፍሰ ገዳዩ ከአንቺ ታካሚዎች መሀከል ሊሆን አይገባውም” ብሎ በባልደረባው እና በተመርማሪዋ መሀከል ያለውን ውጥረት ከዚህ በላይ እንዳይከር በማሰብ “የምታስታውሻቸው ጠላቶች አሉሽ ዶክተር? የሆነ ሰው አንቺን እና በአንቺ ዙሪያ የሚገኙ ሰዎችን ሁሉ ሊጎዳ የሚችል ሰው ይኖራል ብለሽ ታስቢያለሽ?”

“እረ የለም!” ብላ ኒኪ በመዳፏ አይኗን አሸች፡፡ “የሉም እንዲያውም እንደዚህ ያለ ሰውን አላስታውስም፡፡ ምን አይነት ጠላቶች ናቸው?”
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_አስራ_ሶስት

#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

"አላሁ አክበር....አላሁ አክበር“አለ ኢማሙ የዕለተለን የማለዳ እስላማዊ ፀሎት ሊያደርስ
አስቻለው ዛሬ መንገደኛ ስለሆነ ከእንቅልፉ ያነቃው ዘንድ ሲጠብቀው የነበረ ድምፅ ነው
ልክ እንደነቃ ከአንገቱ ቀና ብሎ ነቅነቅ ሲል አልቀለለውም ከሰውነቱ ልጥፍ ብላ የተኛች ደሴት አለች ሔዋን ተስፋዬ።

በወርሃ የካቲት ሁልታኛ ሳምንት ላይ ሽዋዬ ዲላ ውስጥ አልነበረችም፡፡ለአንድ ሳምንት የሚቆይ አጭር የስራ ላይ ስልጠና ልትካፈል ወደ አዲስ አበባን ሄዳለች። በዚያው ሳምንት በዕለተ ሐሙስ አስቻለው ወደ አዲስ አበበ ሊሄድ ተነስቷል ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዋና መስርያ ቤት የዝውውር ጥያቄ ሊያቀርብ።

በአስገዳጅ ሁኔታ ግንኙነታቸውን ለጊዜው ለማቋረጥ ወስነው የነበሩት አስቻለውና ሔዋን ለዚያች እለት የጋራ ቃላቸውን በጋራ አፍርሰዋል የሸዋዬን አለመኖር አጋጣሚ ተጠቅመው አብረው ለማደር።በዚሁ መሰረት ትላንት ምሽት ላይ አስቻለውና በልሁ ከቤቷ አምጥተዋት ሔዋን በአስቻለው ቤት አስቻለው
አልጋ ላይ ከአስቻለው ገር አድራለች::

አስቻለው መብራት አብርቶ የሔዋንን አስተኛኘት አየት ሲያደርገው አሳዘነችው:: አንድ እግሯን ከጭኖቹ መሀል አስገብታ፤ በግራ እጇ አንገቱን አቅፋ በቀኝ
እጇ ደግሞ ወገቡ ላይ ጥምጥም ብላ ተኝታለች፡፡ ከአንገቱ፡ ቀና ብሎ ለአፍታ ያህል ቁልቁል ሲያያት ቆየና ግንባሯ ላይ ሳም አደረጋት
ምናልባት በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆና የእስቻለው እንቅስቃሴ ተሰምቷት ሳይሆን አይቀርም ሔዋን አይኗን ገለጥ ስታደረግ ሁለቱም ተያዩ

«ነጋ እንዴ አስቹ?» ስትል ጠየከቸው
«እረፍዶ!!»
ሔዋን ከአንገቷ ቀና ብላ ወደ መስኮት አየት ስታደርግ የውጭ ብርሃን የለም:: ዋሽህ' ብላ ተመልሳ ተኛች::
«ለኔ ማለቴ እኮ ነው መንገደኛ አይደለሁ!»
«ህልም እያ'የሁ ነበር አስቹ፣»
«ጥሩ ወይስ መጥፎ?»
«የት እንዳለሁ አይታወቀኝም፣ ግን እናትህ ይመስሉኛል። እፊቴ ቆመው ልጄን ከምታመጭበተ አምጪ! የት ነው የደበቅሽው? ኋላ አንድ ነገር ቢሆን ነገ ከአንቺ ራስ ላይ አልወርድም" ይሉኛል::
«ምን አልሻት ታዲያ? አላት አስቻለው እንደ መሳቅ እያለ፡፡»
ምንም! ዝም ብዬ ሳያቸው ከእንቅልፌ ነቃሁ::
«አትዋሺ! አለና አስቻለው አሁንም በቀልድ ዓይነት «ይኼኔ ልጄን
አምጪ ስትልሽ አልሰጥም የት ነው የደበቅሽው ስትልሽ ልቤ ውስጥ ኋላ ልጁ አንድ ነገር ቢሆን» ስትልሽ ደግሞ የግድ የለዎትም እኔ ጋር የተቀመጠ ነገር
አይበላሽም ብለሻት ይሆናል::» አለና ለራሱ እየሳቀ ሔዋንንም አሳቃት፡፡

አስቻለው ሳቁን ከጨረሰ በኋላ ወደ ቁም ነገር በመመለስ ይኼኔ እናቴ በህይወት ብትኖርልኝማ ኖሮ ብዙ ችግርቼ በቀላሉ ይፈቱ ነበር፡፡ በተለይ አንቺን የመሰለች ምራት በማግኘቷ እየተደሰተች አንቺን በማለቴ ስለተፈጠረብኝ ችግርም
መላ ትፈልግልኝ ነበር፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው፤ እኔም እሷም ሳንታደል ቀረንና በልጇ ሀዘን ተቃጥላ ሞተች፡፡» አላት እውነትም በመጥፎ ትዝታ ፊቱን እየከፋው።
«ልጅ ሞቶባቸው ነበር፡፡»
«ያውም የኔ ታላቅ ! እሷንም እኔንም በገንዘብ ይረዳ የነበረ እውሮች ለምን አየህ?» ብለው ገደሉት፡፡ አላት፡፡
«እውሮች!» አለች ሔዋን አባባሉ ግራ ገባ ብሏት።
«ዓይን ቢኖራቸውም "ማስተዋል የጎደላቸው ህሊና ቢሶች፡፡ እስና ያን አሰቃቂ የቀይ ሽብር ዘመን በዓይነ ህሊናወኑ ለአፍታ ያህል ዳሰስ አደረገው::
«እየነጋ ነው ሔዩ፡» አላት ከሃሳቡ መለስ ሲል፡፡
«ትሄድ አስቹ?»
«በቅድሚያ ግን የወጭ በይኝ፡፡» ብሎ ዓይኖቹን ፈዘዝ አድርጎ ሲመለከታት ምላሹን ሰጠች። አንገቱን እቅፍ አድርጋ ከንፈሮቿን በነከንፈሩ ላይ ጣል አደረገቻቸው፡፡ ወሰዳት፡፡ ወስደችው:: ዓይኖቻቸው ተስለመለሙ፡፡ ሰውነታቸው ሞቀ፡፡ ገላቸው ተጣበቀ። ትንፋሻቸው በረከተ። በስሜት ባህር ወስጥ ሰጠሙ፡፡
ምድር ላይ ሆነው ገነትን ለአንድ አፍታ ተመላለሱባት፡፡ ከስሜት ገዞ መልስ እስቻለው ከእልጋ ላይ ወረደ:: ታጠበ፡፡ አበጠረ፡፡
ለባብሶ የመንገድ ሻንጣውን ትከሻው ላይ አነገተና አልጋው ስር ቆሞ ሔዋንን ቁልቁል እየተመለከተ ከአዲስ አበባ ምን ገዝቼልሽ ልምጣ ሔዩ?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ምንም አስቹ!››
«ለምን? ጫማ ልብስ' ወይም ሌላ ነገር ብገዛልሽስ»
«ማን ገዛልኝ ብዬ ልለብሰው አስቹ?» አለችው አልጋው ላይ በክንዷ ደገፍ ብላ ከእንገቷ ቀና በማለት እየተመለከታችው፡፡ አስቻለው የዘነጋው ነገር ነበር፡፡ እንደ አዲስ ትዝ ብሎት ድንገት ቅስሙ ስብር ከለና ለአፍታ ያህል በሀዘን አይን ተመለነታት፡፡
«እንተ ብቻ በሰላም ተመለስ፡፡» አለችው ሔዋን ዓይን ዓይነን እያየች።
«አሜን የኔ ፍቅር» ብሏት ሳም አድርጎ ተሰናበታት፡፡
ሰአቱ ገና ማለዳ ስለነበር ሔዋን ወዲያው አልተነሳችም፡፡ አልጋው ላይ ጋለል ብላ ጣሪያ ጣሪያ እያየች አስተዳደሯን በትዝታ ታየው ጀመር፡፡ ደስ የሚል ሌሊት ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ አስቻለው ቃሉን ማክበሩ አስደስታት:: ለግማሽ ሌሊት ያህል ከንፈሮቻቸው ሳይላቀቁ፤ በመተሻሸት ብዛት በስሜት ሲፈራገጠ ያላደሩትን
ያህል አስቻለህ ለአንዴ እንኳ ወደ ጭኖቿ መሃል ሳያመራ በማደሩ ከልቧ አደነቀችው:: ከመቸውም ጊዜ በላይ በእሱ ላይ ያላት እምነት የፀና ሆነ፡፡ ያ ሌሊት
ሔዋን ሴት እንደመሆኗ ወንድ እንደሚያስፈልጋት በውል የተረዳችበትም ነበር!
ከሆንም አስቻለው ፍስሀ ብቻ!
ሔዋን መልካም የፍቅር ተስፋ የምታይበት አዕምሮዋን ስጋትም ጠቅ ያረገው ነበር፤ ከሁሉም በላይ እህቷ ሸዋዬ በሁለቱ ፍቅር ላይ ያላት መጥፎ አመለካከት፡፡ ከዚያ ቀጥሎ ለቤተሰቦቿ የጻፈችባት ደብዳቤ፡፡ ሁለቱም እንደ ትልቅ የፍቅር እንቅፋት ያሰጓታል፡፡ ያስጨንቋታል። ለመሆኑ አስቻለው የዝውውሩ ጉዳይ ቢቀናውስ! ወደ ሄዴበት ቦታ አብራው ትሄድ ይሆን! በምን ሁኔታ ጠፍታ ወይም በቤተሰቦቿ ፈቃድ የሚታወቅ ነገር የለም። ይህም እንዱ የሀሳቧ ዘርፍ ነበር፡፡

በዚህና በመሳሰሉት የፍቅር ጉዳዮች ዙሪያ ስታወጣ ስታወርድ ሳታውቀው እረፍዶ ኖሯል፥ በግምት ወደ አንድ ሠዓት ተኩል አካባቢ ተጠግቷል። የጠዋት
ፈረቃ ተማሪ ናትና ፈጥና ተነሳች፡፡ የአስቻለውን አልጋ ስምር አድርጋ
አነጣጠፈች፡፡ ታጥባ ፀጉሯን ጎነጎነች በኮመዲኖው ላይ የተቀመጠ የአስቻለውን
ፎቶ ግራፍ ሳም ሳም አድርጋ ቤቱን ቆላልፋ ወጣች፡፡ ከዛም ወደ ቤቷ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አስቻለው ከሾፌሩ ኋላ ሦስት ሰዎችን በሚያስቀምጠው የመጀመሪያ ወንበር ላይ በሁለት ሰዎች መካከል ተቀምጦ ወደ አዲስ አበባ ይጓዛል በጎራ በኩል የመስኮት ጥግ ይዘው ዕድሜያቸው ወደ ሀምሳዎቹ የገባ የሚመስል፤ ነገር ግን በምቾት ኑሮ ፊታቸው ደንቡሽቡሽ ያለ ቀይ መልከ መልካም ሴት ተቀምጠዋል፡፡ የጥቁርና ነጭ
ቡራቡሬ ቀሚስና ባለ ጥለት ነጭ ነጠላ ለብሰዋል። እራሳቸውን
በጥቁር ሻሽ ሽክፍ አድርገው አስረዋል። ከቀኙ በኩል ደግሞ አንዲት ዕድሜዋ ከአስራ ሰባት ዓመት የማይበልጣት ጠይም ልጃገራድ ተቀምጣለች፡፡ ነጣ ያለ ጉርድ ቀሚስ በቀይ ሹራብ ለብሳለች። ስልክክ ያለች የጠይም ቆንጆ ናት። ሦስቱም እየተጨዋወቱ ይጓዛሉ።
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....ምንትዋብ ማረፊያ ክፍሏ ቆይታ ማታ ላይ ራት ከበላች በኋላ፣ በሁለት ደንገጡሮች ታጅባ ወደ አፄ ፋሲል ቤተመንግሥት አቀናች። ደረጃውን ከወጡ በኋላ፣ ሁለት ያደገደጉ ደጅ አጋፋሪዎች መግቢያው በር ላይ ቆመው ለጥ ብለው እጅ ነሥተው መግቢያው ላይ ባለው በወንዶች የግብር አዳራሽ በኩል እንዲሄዱ መሯቸው።

ምንትዋብ ቆም አለች።

የግብር አዳራሹ ወለል ከፋርስ በመጣ ምንጣፍ አሸብርቋል። በክፍሉ ዙርያ ያሉት ባለመስተዋት መስኮቶች በሐር መጋረጃዎች ተሸፍነዋል ::በፋና ወጊዎች የተለኮሱት በየማዕዘኑ የተቀመጡት ትልልቅ ጧፎች
ክፍሉን አድምቀውታል።

ምንትዋብ ባየችው ሁሉ ተማረከች።

ሴቶቹ ግብር አዳራሽ ስትገባ ተመሳሳይ ድምቀት አይታ ሦስተኛ
ደርብ ላይ ወደሚገኘው የንጉሠ ነገሥቱ መኝታ ክፍል ለመግባት ደረጃ ስትወጣ፣ ደንገጡሮቹ እጅ ነሥተዋት ከኋላዋ ተመለሱ።

ደረጃውን ወጥታ ስትጨርስ፣ አፄ በካፋ ቀን አድርገውት የነበረውን
ዘውዳቸውንና ካባቸውን አውልቀው፣ ማምሻ ክፍል ውስጥ፣ ቀይ ከፋይ የለበሰ ሰፊ ወንበር ላይ ተቀምጠዋል። ከፊት ለፊታቸው ያለ ጠረጴዛ ላይ፣ ጠጅ በብርሌ ተቀምጧል። በክፍሉ ጥግ ጥግ የቆሙ፣ ረጃጅም
መቅረዞች ላይ የተቀመጡት ማሾዎች ለክፍሉ ልዩ ውበት ሰጥተውታል።

አፄ በካፋ፣ ምንትዋብ ስትገባ፣ በፈገግታ ተቀብለዋት፣ ከጎናቸው
ያለ ወንበር ላይ እንድትቀመጥ በእጃቸው አሳይዋት። ስትፈራ ስትቸር ተቀመጠች። ዐይናቸውን ማየት አቃታት።

እሳቸው ግን በእዚያ ምትሐታዊ ውበቷ ዳግም ተማርከው ዐይናቸውን ከእሷ ላይ ማንሳት ተስኗቸዋል። ወዲያው ግን መርበትበቷን አስተውለው፣
“አይዞሽ የኔ ዐይናማ፤ ምንም ሚያስፈራ ነገር የለም እኮ” አሏት፣ እጇን እጃቸው ውስጥ አድርገው።

አቀርቅራ ዝም አለች።

“ያረግሽልኝን ሁሉ መቸም አልረሳውም። ኸኪዳነ ምሕረት ጋር አስታመሽ አዳንሽኝ። የልዥ አዋቂ። ኪዳነ ምሕረት ታክብርሽ።
እንዳው ነገሩን ሁሉ ሳጤነው... እዝጊሃር እንድንገናኝ ፈልጎ ነው እንጂ ኸናንተ ቤት ታምሜ መምጣቴ ተጎድቸ ነበር፤ ኪዳነ ምሕረትና ሩፋኤል እንዳንቺ ባለች ዐይናማ ካሱኝ” አሉ፣ በሠርጋቸው ማግስት ስለሞተችው ሚስታቸው አስበው።

ምንትዋብ እጇን እያፍተለተለች ዝም ብላ አዳመጠቻቸው።
በተናገሩት ነገር ልቧ ተነካ። እኛ እንደዛ በወርቅና በዕንቁ ተንቆጥቁጠው፣ሩቅ ይመስሉ የነበሩት ንጉሠ ነገሥት እንደ እሷው ሰው መሰሏት።

“እስቲ ያነን ሚጥም ድምጥሽን አሰሚኝ፤ ተጫወቺ እስቲ። ኸናንተ
ቤት ሳለሁ ላነጋግርሽ እየፈለግሁ ማን መሆኔ እንዳይታወቅ ብየ ዝም አልሁ። ኸኛ ኸደግ አባትሽ ጋር ስንኳ ሳልጫወት ተመለስሁ” አሏት።

የምትለው ጠፋት። በመጨረሻ፣ ቁስቋም ታክብርልኝ። ለዝኽ
ላበቁኝ ለርሶም፤ እሷው ምላሹን ትስጥዎ” አለቻቸው።
“እኔ ምን ለዝኸ አበቃሻለሁ። ሁለተኛ እንዲ ስትይ እንዳልሰማ።
ሚገባሽ ቦታ ነው የመጣሽ። እኼ ደሞ ቤትሽ ነው፤ ቀስ እያልሽ ሁሉን ትማሪያለሽ። ሚቸግርሽ ነገር ሲኖር ሳትፈሪ ንገሪኝ። ደንገጡሮችሽም አሉ። ለኔም ኸንግዲህ ኻንቺ ሌላ ሚቀርበኝ የለም” አሉና ቀስ ብለው
ተነሥተው፣ ቀኝ እጇን ይዘው፣ መኝታ ክፍል ውስጥ ይዘዋት ሲገቡ፣ በአጎበር የተሸፈነውን ተደራራቢ የእንጨትና የጠፍር አልጋ ስታይ፣ ልቧ ተንተረከከ።

ይሁን እንጂ፣ ልጅነቷ ማክተሙን ብቻ ሳይሆን፣ የዚያን ዕለት
የጀመረችው ግንኙት ሕይወቷ የሚጓዝበትን መንገድ ዳግም እንደጠረገ አላስተዋለችም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም።”

ሰኞ ጠዋት ጥላዬና አብርሃ አለቃ ሔኖክ ቤት ሲደርሱ ባለቤትየዋ
ወጥታ ተቀበለቻቸው። ውስጥ ሲገቡ ሰባዎቹ መጀመሪያ ያሉ፣
የግርማቸው፣ የብልኅነታቸውና የደግነታቸው ድባብ የሚያስተጋባ
አዛውንት መደብ ላይ ተቀምጠው ብራና ላይ የተጻፈ ጸሎት ያነባሉ።
የጥምጥማቸው ንጣት አካባቢውን ደመቅ አድርጎታል።

“የዠመሩትን እስቲጨርሱ ነው። ዐረፍ በሉ” አለቻቸው ባለቤቲቱ፣
ከአለቃ ሔኖክ ፊት ለፊት ያለ አጎዛ ጣል የተደረገበት መደብ በእጄ
እያሳየቻቸው።

ጥላዬ፣ አለቃ ሔኖክን በፈገግታ ከላይ እስከታች ተመለከታቸው።
ቀልቡ ወደዳቸው፣ ከእሳቸው ዘንድ ጉዳዩ እንደሚቃናለት አንዳች ነገር ነገረው። ከእሳቸው ሌላ ማንም ባያስተምረው ፈለገ። ቤቱን ሲቃኝ፣ ጥግ ላይ ካለው የጠፍር አልጋ በስተቀር እምብዛም ዕቃ አይታይበትም።ከአልጋው ግርጌ የቀለም ቀንዶች፣ የቀርከሀ ስንጥሮች፣ ብራናና በዕራፊ
ጨርቅ የተጠቀለሉ ዱቄት መሳይ ነገሮች ተቀምጠዋል። ይህንን
እየተመለከተ ሳለ አለቃ ሔኖክ፣ “አድራችሁ ነው ልጆት?” ሲሏቸው
ከአብርሃ እኩል ብድግ ብሎ ለሰላምታቸው የአክብሮት ዐጸፋ መለሰ።

“ምን ፈልጋችሁ ነው?” በሚል ዓይነት ሲያይዋቸው አብርሃ፣ “እሱ
ኸቋራ ነው የዘለቀ። ሥዕል መማር ፈልጋለሁ ቢለኝ ኸርሶ ዘንድ
ይዠው መጣሁ” አላቸው።

“መልካም... ሥዕል ለመሣል ቅኔ መማር አለብህ። ሞካክረኻል?”
“ወፍታ ጊዮርጊስ የንታ አምሳሉ ዘንድ ሥላሤ አድርሽ... ወዲህ
መጣሁ።”
“ሥዕል ሥለህ ታውቃለህ?” አሉት፣ ትክ ብለው እያዩት። ዞር አሉና፣ ምድጃ ላይ ድስት ጥዳ የነበረችውን ባለቤታቸውን፣ “ወርቄ እስቲ ሚቀመስ ታለ፤ ለዛሬ ዕንግዶቻችን ናቸው እኒኸ ተማሮች” አሏት።

ጥላዬ፣ ለጠየቁት ጥያቄ አዎም የለም አልሣልኩምም ማለት ፈለገና አመነታ። ዐይናቸው እሱ ላይ ተተክሎ ሲቀር፣ “ጥቂት ሞካክሬአለሁ፤ ግና ብራና ላይ ማይዶል” አላቸው።

“ዛዲያ ኸምን ላይ ሣልህ?”
ሊናገር ፈልጎ ዐፈረ። እሳቸው መልስ ፈልገው ተጠባበቁ። ያን
ችምችም ያለና ወተት የመሰለ ጥርሱን ብልጭ አደረገና፣ “ግድግዳ
ላይ” አላቸው።
“ግድግዳ ላይ? ግድግዳ ላይ እኮ ማነም ተነሥቶ አይሥልም።”
እንጀራ በድቁስና ጠላ ይዛ የመጣችው ወርቄ ከት ብላ ሳቀች። ያን ጊዜ ሁሉም፣ አለቃ ሔኖክ ጭምር ሳቁ። ጥላዬ፣ ወርቄ ጠላውን መጀመሪያ
ለአለቃ ሔኖክ ከዚያም ለእሱናኸ ለአብርሃ ቀድታ እስክታስቀምጥ
ጠበቀና፣ “ኸቤታችን ግድግዳ ላይ ነው። በእናቴ ወንፊት ዐመድ
እየነፋሁ፣ በውሃ ለቁጨ ሳበቃ ኸቤታችን ዠርባ ግድግዳ ላይ በእናቴጸ አክርማ እሥላለሁ። አባቴ ሲያዩት ይቆጣሉ። ግድግዳውን መልሰው
በጭቃ ያስመርጉታል” አለ።
ወርቄ እንደገና ከት ብላ ሳቀች፤ ሁሉም አብረዋት ሳቁ። ጥቂት
ቆይታ በድቁስ ከቀረበው እንጀራ ላይ ግማሹን ተቃምሰው መተዋቸውን ተመልክታ ለጠላው ማጣጫ በአነስተኛ ጮጮ ላይ ቆሎ ይዛ መጣች።

አለቃን አዘግናቸው እነጥላዬን፣ “እየቆረጠማችሁ” ብላ አስቀምጣላቸው ሄደችው ።
አለቃ ሔኖክ ከዘገኑት ቆሎ ላይ ቆንጠር አድርገው አፋቸው
አደረጉና፣ “ሥዕል መሣልህ ነው ወይስ ግድግዳ ላይ መሣልህ ኣባትህን ሚያስቆጣቸው?” ሲሉ ጠየቁት።

“ወታደር መሆን አለብህ እያሉኝ... ሥዕል እንድሥል አይፈልጉም።
በቅኔውም ቢሆን እንድገፋ አይፈልጉም። እሳቸው እስታሉ ድረስ አገሬ አልመለስም ብየ ጠፍቸ ወዲህ ዘለቅሁ።”

አለቃ ሔኖክ ራሳቸውን ነቀነቁ፣ መሆን የለበትም በሚል ዓይነት።
“ላባትህ መልክትም ቢሆን ላክባቸው። ያዝናሉ። እናትህም ቢሆኑ በልቅሶ ይሞታሉ። ብዙዎቻችን ለትምርት ብለን ጠፍተን ነው ኸቤት ምንወጣ ግና ኋላ እንመለሳለን። አባትህ ላንተ ሌላ ተመኙ፣ ከንተ ደሞ ሌላ ፈለግህ። ክፋት የለውም። ባባትህ ቂም እንዳትይዝ። ለማንኛውም
#ትኩሳት


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

#እንደወረደ_ነውና_ለአንባቢ
#የማይመቹ_እና_ፀያፍ_የምንላቸው
#ቃላቶች_አሉትና_አሁንም
#በድጋሚ_እንደምናገረው
#የማይመቸው_እንዳታነቡት
#እመክራለሁ

በጣም ፀያፍ ቃሉት አሉት

ኒኮል
ፍትወት


ባህራም ወደ ጋርደን ሲሄድ ኒኮልን ብቸኝነት እንዳይሰማት አደራችሁን ብሎን ሄደ በተለይም ሉልሰገድን አደራ አለው፡፡ ኒኮል
አይናፋርና ሰውን ቶሎ የማትላመድ በመሆኗ ከሉልሰገድና ከጀምሺድ ጋር ብቻ ነበር በመጠኑ የምትጫወተው

አንድ ምሽት ከእራት በኋላ፣ እኔ፣ ሉልሰገድ፣ ጀምሺድ፣ ተካ ካፌ ዶርቢቴል ቁጭ ብለን የሲኒማ ሰአት እስኪደርስ ስናወራ፣
ኒኮል ግራጫ ሱፍ ኮትና ጉርድ ከአረንጓዴ ሸሚዝ ጋር ለብሳ መጣች ሉልሰገድ ተነስቶ ከሌላ ጠረጴዛ ወምበር ሲስብላት፣
ጀምሺድ ተነሳና Bon soir ብሎ ሊጨብጣት እጁን ዘረጋ Bon soir ብላ እጇን ሰጠችው ጨበጣት

«አይ!» ብላ እጇን ማሻሸት ጀመረች

«ምንድነሽ?» አላት «ምን ሆንሽ?» ማለቱ ነው

«ወጋኸኝ» አለችው፣ ሉልሰገድ ያመጣላት ወምበር ላይ
እየተቀመጠች

«እንደት ወጋሁሽ?»

«በሀይል ጨበጥከኝና ቀለበቴ ወጋኝ»

«ኦ!» አለና፣ ይቅርታ እንደመጠየቅ ዛሬ ከሰአት በኋላ የሚከራይ አፓርትመንት ቤት እየፈለግኩ ብቻዬን» አለ። ትንንሽ ሰማያዊ አይኖቹ እንደልማዳቸው በሳቅ ይጨፍራሉ፡፡ ቀጠለ፡-
አንድ አፓርትመንት ፎቅ ወር ማለቴ ወጥቼ፣ የባለቤት የበር
ደወል። በእጄ መግፋት ውስጥ ደወል። ቀጭን ደወል ኪል! ኪል
ቆንጆ ደወል። በር ክፍት! የደወልኩት በር አይደለም፡፡ ሌላ በር:: ከግራ በኩል ከበሩ ብቅ። አንድ ሽማግሌ ዶክተር። ነጭ የዶክተር ልብስ። በአይኑ መነፅር በራሱ መላጣ በከንፈሩ ሙስታሽ በእጁ መርፌ

ዶክተር እኔን «ወዲህ ይግቡ፣ ልውጋህ»

እኔ «እኔ መርፌ አይፈልጉም። እኔ በሽታ የለም። እኔ ጤነኛ
እኔ ቤት መፈለግ፡፡ የአፓርትመንት ባለቤት መፈለግ። ለቤት
ኪራይ፡»

ዶክተር «ግድ የለህም፡፡ ና ግቡ ልውጋህ፡፡ እኔ አዋቂ መርፌ
ወጊ ብሉ መርፌ እንደ ጋንግስተር ሽጉጥ ወደኔ እኔ ዶክተር! እኔ አሁን መርፌ አይፈልጉም፡፡ ነገ እመጣለዚህ
እሺ?
ዶክተር «እኔ ነገ አይሰሩም። አሁን ና ልውጋህ፡፡ በኋላ ይቆጭሀል አላስከፍልም፡፡ አሁን ልውጋህ። ነገ ሀይድሮጅን ቦምብ ፓሪስ ላይ ፑፍ!

እኔ «ዶክተር፣ አሁን መጣሁ» ብዬ በሩጫ ፎቁን መውረድ
ዶክተር በሀይል ጩኸት ድምፅ ታድያ እኔ ማንን ይወጋል?
አንተ ከሄድክ እኔ ማንን ይወጋል?»

እኔ መልስ አልሰጥም ለዶክተር፡ በልቤ «እንጃ፣ ምናልባት ከኔ
በኋላ ሌላ ሰው አፓርትመንት ፈላጊ። ደወል ሲደውል ኪል! hል!
ዶክተር ቅስ ብሉ መርፌ ጠቅ! ከኋላ፡፡»

ጀምሺድ ሲያስቀን ከቆየ በኋላ ሁላችንም ሲኒማ ሄድን። አንድ
ነገር አስተዋልኩ፡፡ ሉልሰገድ በትልልቅ ጥቋቁር አይኖቹ ኒኮልን
ያያታል። ኒኮል በአረንጓዴ አይኖቿ ጀምሺድን ታየዋለች። ጀምሺድ
በብልጮ ሰማያዊ አይኖቹ ማዳም ፖልን ያያታል። ማዳም ፖል ብጫ ቅብ ፀጉሯን እያብለጨለጨች ወፍራም ዳሌዋን እያወዛወዘች
በጠረጴዛዎቹ መሀል ጉድ ጉድ ትላለች፡፡ አንድ ጊዜ ከጀምሺድ ኋላ ስታልፍ መንገዷን የዘጋባት አስመስላ ትከሻው ላይ እጆቿን አሳረፈችና "Pardon monsieur" አላቸው "Derien madame" ብሎ አሳለፋት፡፡ ብዙ ጊዜ እየከበብነው ሲያስቀን ስለምታይ፣ አይኗን ጣል
አድርጋበታለች። መስየ ፖል በሩ አጠገብ ቆሞ ገንዘብ እየተቀበለ
ሀጂውን ሰው በየዋህ ድምፅ
“Au revoir!' ወይም “A bient” ይላል

አማንዳ ወደ አገሯ እንደሄደች ሉልሰገድ አንዲት ኢጣልያዊት
ልጅ ያዘ። ትምህርት ተጀምሮ ጥቂት ሳምንት እንዳለፈ ልጂቱ
አረገዘች። የፈረንሳይ ህግ ማስወረድ ስለሚከለክል፣ ሉልሰገድ ከኔ፣ ከጀምሺድና ከሌሎች ገንዘብ ተበድሮ ልጅቱን ወደ ስዊስ አገር ላካት። በዚያው አገሯ ገባች።

አንድ ቀን፣ ባቡር ጣቢያው አጠገብ ያለችው ትንሽ ካፌ በረንዳ
ላይ ቁጭ ብለን፣ ሉልሰገድ የሚወደውን ቡና አይነቱን የስኮትላንድ ቢራ እየጠጣን ስናወራ፣ ድንገት ተነሳና «ቆየኝ መጣሁ። ካልመጣሁ
ቤትህ እንገናኝ ብሎኝ፣ ባቡር መንገዱን ተሻግሮ ሁለት ኮረዳዎችን አቆመና ትንሽ አነጋገራቸው። ተለይተውት ሲሄዱ መሬት መሬቱን እያየ ወደኔ ተመለሰ

«እምስ የሸተተኝ መስሉኝ ነበር፡፡ ተሳስቼ ነው » አለኝ፡፡ አንድ
ነገር ሊነግረኝ እንደፈለገ ታወቀኝ፡፡ ዝም አልኩና ቢራውን ቀዳሁለት። ጎልዋዝ ሲጋራ አፉ ላይ ሲሰካ፣ ክብሪቱን ከጠረጴዛው ላይ አንስቼ አቀጣጠልኩለት መከራ ነው ባክህ። ሴቶቹ እምቢ አሉኝ። እንደዚህ ሰሞን እምስ ቸግሮኝ እያውቅም፡፡ እኔ ደሞ እንደምታውቀኝ ነኝ፣ ያለሱ
መኖር አልችልም፡፡ ለኔ መንግስተ ሰማያት ማለት በየሜዳው ላይ፣
በየዛፉ ስር፣ በየመንገዱ ዳር፣ በየግድግዳው ጥግ እምስ የሚበቅልበት አገር ነው:: ገሀነም ደሞ ፈፅሞ እምስ የማይገኝበት እርኩስ ቦታ ነው:: እምስ ዘርተውት ቢበቅል ኖሮ ገበሬ እሆን ነበር፡፡»

ሌላ ቢራ አዘዝኩለት

«እኔ ምልህ! ስለኒኮል ምን ይመስልሀል?» አለኝ
«ምንም»
“ምንም? እንግዲያው አታውቅም»
“ምን ማለትህ ነው?»
«እኔ እንደሷ ያለች ሴት አጋጥሞኝ አያውቅም:: አየህ፣
መጀመርያ ስታያት ስሜት አትሰጥህም፡፡ አመዳም ፀጉር የኔ
አይነት ጥቃቅን ጥርስ፣ የደረቀ ከንፈር፡፡ ታድያ እየለመድካት
እየለመድካት ስትሂድ ደሞ ስትለያት ትናፍቅሀለች። ታድያ ጤነኛ ናፍቆት አይደለም፡፡»

«ዋ! አንተ ልጅ፣ ፍቅር የያዘህ ትመስላለህ»

«ፍቅር አይደለም። ቅንዝር ነው፡፡ የሚያቅበጠብጥ ቅንዝር::
ባህራምን እወደዋለሁ፡፡ ጎበዝ ስለሆነ አደንቀዋለሁ፡፡ ደሞ አምኖን አደራ ኒኮልን አጫውታት ብሎኝ ነው የሄደው:: ግን አልቻልኩም። በጭራሽ አልቻልኩም፡፡ እኔ ልለምናት ነው»

«እምቢ ብትልህስ?»

«የምትለኝ አይመስለኝም። እሷም የምትፈልገኝ ይመስለኛል።
ትላንትና ማታ ሲኒግ ወስጃት፣ ፊልሙን አላየሁትም፡፡ ሽቶዋ
ከለከለኝ፡፡ ቀስ ኣድርጌ እጄን ጭኗ ላይ አሳረፍኩ፣ አልገፋችኝም።
ትንሽ ቆይቼ እጇን አመጣሁና የተገተረ ቁላዬ ላይ አስቀመጥኩት።
በሱሪው ላይ፡፡ እጇን እዚያው ተወችው። ታድያ ክፋቱ፣ በጭራሽ
አላሻሸችኝም፡፡ እጄን ወደ ቀሚሷ ውስጥ ላስገባ ስል ከለከለችኝ።
ለመከልከል እጇን ከቁላዬ ላይ አነሳች፡፡ እንደገና መድፈር
አልቻልኩም፡፡ ... ስቃይ ነው የኒኮል ነገር፡፡»

ከአራት ቀን በኋላ ሉልሰገድ ኒኮልን አፍ አውጥቶ፣ “ፍቅር ይዞኛል ቤትሽ መጥቼ ልደር?» አላት
«አኔ እሺ አልልህም። ግን እሺ ብልህም በኋላ ለባህራም
እነግረዋለሁ» አለችው::
ለምን ቢላት
«ባህራምን ላታልለው
አልፈቅድም» አለችው
«ከባህራም ጋር መፋረስ አምሮሽ እንደሆነ አንቺው ራስሽ
ምክንያት ፈልጊ እንጂ እኔን ሰበብ እንድታደርጊኝ አልፈቅድልሽም
እላት ሉልሰገድ ይህን ሲያጫውተኝ ሆ! ባህራምን ለምን እንጀራ ከምታበላው ሴት ጋር ላጣላው? ምን በደለኝ?» አለ
«እንግዲያው ምን በደለህና ኒኮልን ልትበዳበት ትፈልጋለህ?”
አልኩት እየሳቅኩ

«በጭራሽ አንድ አይደለም» አለኝ መጀመርያ ነገር ብበዳት አያልቅበትም። እንኳን ልጨርስበት አላሰፋበትም፡፡ አንድ ቀን
ገላውን ታጥቦ ሙታንቲውን ሲቀይር አይቼ፣ ጀላ ነው የተሸከመው። የኔ ግትር ብሎ ቆሞ እንኳ ያንን አያክልም፡፡ ታድያ ተኝቶ ተንጠልጥሎ ነው ያየሁት። እናትክን! ምናባክ ያስቅሀል? እኔን አይቶ ሊቆምበት ኖሯል?»
#ሳቤላ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ

...እነዚያ አስከሬን አጋችዎች ግን ሊወጡ አልቻሉም " ሚስተር ካርላይል አስከሬኑ ወዶ ነበረበት ክፍል ገብቶ ማንነታቸውንና በምን መብታቸው እንደዚያ ማድረግ እንደቻሉ ጠየቀ መረመረ እንደዚህ ያለ ድፍረት በሕይወቱ ዘመን አይቶ አያውቅም " ብቻ ዱሮ አንድ የቤተ ክህነት ባለሥልጣን የሆነ ሰው እንደዚሁ በከባድ ዕዳ እንደ ተዘፈቀ ሞተና አስከሬኑ ሊቀበር ቤተ ክርስቲያን እንዶ ደረሰ እንደዚሁ ባለዕዳዎች ይዘውት እንደነበር አባቱ ያጫወተውን ያስታውሳል " አሁንም እነዚህ ሰዎች የጠየቁትን ከባድ ገንዘብ ካልተከፈላቸው ሚስተር ቬን ተተኪው የማውንት እስቨርን ኧርል ከካስል ማርሊንግ እስኪደርስ ድረስ ሬሳውን መልቀቅ
እንደማይችሉ አስታወቁ "

በበነጋው ጠዋት እሁድ ሚስተር ካርላይል ከቤቱ ዌስትሊን አድሮ ወደ ኢስት ሊን ቢመጣ ማንም አልደረሰም። ሳቤላ ከቁርስ ክፍል ተቀምጣ ሰውነቷ ይንቀጠቀጣል የቀረበውን ምግብ አልነካችውም መልኳ ሁሉ የበሽተኛ መስሏል ሚስተር ካርላይል ሁኔታዋንና የበሽተኛ መስሏል ሚስተር ካርላይል ሁኔታዋንና የበሽተኛ ገፅታዋን አይቶ ዝም ሊል ስላልቻለ ጠየቃት።

"አልተኛሁም በጣም በርዶኛል" በጣም ከመፍራቴ የተነሳ ዓይኔን ላመል ያህል እንኳን ሳልከድን እንዲችሁ እንዳለሁ ነገ።

"ምኑ ነው ያስፈራሽ?"
እነዚህ ሬሳውን የያዙት ሰዎች አለችው ሹክ ብላ የሚስተር ቬን አልመድረስም ገርሞኛል።

« ፖስታ አልመጣም ? » አላት "

« እንጃ እስካሁን የደረሰኝ ነገር የለም »

ገና ተናግራ ከማብቃቷ የቤቱ ዋና አሽከር አንድ ማቅረቢያ ሙሉ ደብጓቤዎች ይዞ ገባ " ብዙዎቹ ለሳቤላ የተላኩ የኀዘን መግለጫዎች ነበሩ " አንድ የማርሊንግ ከተማ ማኅተም የነበረበትን ደብዳቤ መርጣ አነሣችና • « ይኸ የሚስዝ ቬን ጽሕፈት ነው » አለችው ለሚስተር ካርላይል "

« ካስል ማርሊንግ ቅዳሜ »

« ለምወድሽ ለሳቤላ በጀልባው ሽርሽር ስለ ሔደ እኔ ከፍቸ የያዘውን መልዕክት ባየሁት ጊዜ በጣም አዘንሁ እሱ ግን ባሁኑ ስዓት ያለበትን ቦታ በትክክል አላውቅም ነገር ግን እሑድ
እንደሚመለስ ነግሮኛል " ብዙውን ጊዜም ቃሉን በመጠበቅ ረገድ ጠንቃቃ ስለ ሆነ በተስፋ እጠብቀዋለሁ " ከደረሰ ደግሞ ወዲያው ወደ ኢስት ሊን እንደሚመጣ አትጠራጠሪ

« ስለ አንቺ የተሰማኝን ኀዘን መግለጽ አልቻልኩም " በጣም ከመረበሼ የተነሣም ከዚህ በላይ መጻፍ አልሆነልኝም " መንፈስሽን ላለመጣልና ራስሽን በራስሽ ለማበረታታት ሞክሪ እያልኩ ልባዊ ኀዘኔን እገልጻለሁ " ያንቺው ታማኝ

"ኤማ ማውንት እስቨርን"

ሳቤላ ፊርማዋን ስታነብ ፊቷ ልውጥ አለ " « ራሷ ከጻፈችው ኤማ ቬን ብላ መፈረም ነበረባት ብላ አሰበች « አዬ አለመታደል » ብላ ወረቀቱን ለሚስተር ካርላይል ሰጠችው "

እሱም የሚስዝ ቬን ሙጭርጭር ጽሕፈት በፈቀደለት ፍጥነት መጠን ተመልክቶ ከፊርማው ሲዶርስ ከንፈሮቹን ሞጥሞጥ አደረገ " ለሳቤላ የተሰማት ለሱም ተሰምቶት ይሆናል "

«ቁም ነገር ያላት ሰው ብትሆን ኖሮ ብቸኝነትሽን ተገንዝባ እሷው እራሷ ገሥግሣ ትመጣ ነበር » አለ ሚስተር ካርላይል ግልፍ አለውና

ሳቤላ እጅዋን ራሷ ላይ አስደገፈች ከፊቷ የተደቀኑት ችግሮች መከማቸት ጀመሩ " ስለቀብሩ ሥነ ሥርዓት የተሰጠ ትእዛዝ አልነበረም » እሷም ብትሆን ለማዘዝ መብት ያላት መስሎ አልታያትም " የማውንት እስቨርን ኧርሎች ሁሉ የተቀበሩት ማውንት እስቨርን ላይ ነበር " ግን የአባቷን አስከሬን እዚያ ድረስ ለማጓዝ ከፍ
ተኛ ወጭ ይጠይቃል ተተኪው ኧርልስ በነገሩ ይስማማ ይሆን ? ካለፈው ጧት ጀምሮ በተጫናት የሐሳብ ክብደት ያረጀች መሰለች " ሐሳቦችዋ ተለወጡ " አስተሳሰቡዋ ቈልምም ብሎ አቅጣጫወን ለወጠ " ክብር ሀብትና ማዕረግ የነበራት ወጣት
እመቤት አሁን ሁኔታዋን ስታስበው ምናምን የሌላት ለማኝ በኖረችበት ቤት ቀላዋጭ መሆኗ ታያት " በፍቅርና በጀብድ ታሪኮች ውስጥ ወጣት እመቤቶችን መልከ መልካሞችና ማራኪዎች ከሆኑ የዕለት ጭንቀትና የአስፈላጊ ነገሮች ችግር የማይታያቸው ረሃብን ጥማትን ብርድንና እርዛትን አስከትሎ ስለሚመጣው
ስለድህነት ጭራሽ ግድ የሌላቸው አድርጐ ማቅረቡ የተለመደ ነገር ሆኗል " በእውነተኛ ኑሮ ውስጥ ግን ነገሩ እንደዚህ አይደለም " ሳቤላ ቬን አባቷን በሌሎች ዘንድ
የተባለ ቢባል ከልቧ ታከብረውና ትወደው ስለነበር በመሞቱ እርር ብላ አዝና ነበር
ይሁን እንጂ በዚህ ኀዘንና ያባቷ ሞት ባስከተላቸው ልዬ በሆኑ ችግሮች መካከል ተወጥራ እያለችም ስለ ወደፊት ዕድሏ ማሰቧን አልተወችም አስተማማኝ ያለመሆኑና ገና አስቀድመው በግልጽ መታየት የጀመሩት ችግርቿ በኀዘኗ ጣልቃ እየግቡ
ይደቀኑባት ጀመር ። ያ ነገሩ ግልጽ የነበረው ባለዕዳ ፡ « አንገትሽን የምታስገቢበት ጣራ የኔ ነው የምትይው አንድ ብር እንኳን የለሽም » ብሎ የተናገራት ከዚያ ወዲህ ከልቧ አልጠፋም በዕዝነ ልቦና ያለማቋረጥ ትሰማዋለች » እስከ ጊዜው ሚስተር ካርላይል ቤት ቆየች ከዚያ በኋላስ የት ነው የምትደርሰው ከማን ጋር ነው የምትኖረው ? አሽከሮቹ ሁሉ ያገለገሉበትን ደመወዛቸውን ይፈልጋሉ " ከየት አምጥታ ትከፍላቸዋለች ? ይህ ሁሉ ጥያቄ በአእምሮዋ እየተመላለስ አስጨነቃት »

« ሚስተር ካርላይል ይህ ቤት ያንተ ከሆነ ምን ያህል ጊዜ ሆነው ? » አለችው ሁለቱም ዝም ብለው ከቆዩ በኋላ ።

« ግዥው የተፈጸመው ባለፈው ሰኔ ወር ነበር ግን ለኔ እንደ ሸጡት አባትሽ አልነገሩሽም ? »

« ምንም አልነገረኝም " አሁን ይኸ ሁሉ ያንተ ነው ማለት ነው ? » አለችው የክፍሉን ዙሪያ በዐይኗ እየቃኘች።

« ወንበርና ጠረጴዛ የመሳሰሉት ሁሉ አብረው ተሽጠዋል “ ልብስና እንዲሁም እንደ ሰሀን የመሳስሉት የቤት ዕቃዎች ግን ከሽያጬ ዝርዝ አልገቡም »

« እንግዲያውማ እነዚያ ትናንት ገንዘባቸው እንዲሰጣቸው ሲጠይቁ የነበሩት ሰዎች ሳይሸጥ በቀረው ዕቃ ላይ መብት ይኖራቸዋል ማለት ነው? »

« እንጃ ለኔ እንደሚመስለኝ እንኳን እንደ ሰሀን 'እንደ ጌጥ ዕቃዎች የመሰሉ ሁሉ ሥልጣኑን የሚወርሰው ሰው ነው የሚረከባቸው »

« ልብሶቼስ የኔ ናቸው ? »

ሚስተር ካርላይል በሳቤላ አጠያየቅ ሣቅ አለና ለማንም ሊሆኑ እንደማይችሉ ነገራት "

« እኔ ምን ላድርግ ? ነገሩ ሁሉ ሊገባኝ አልቻለም " በዚህ የአንድና የሁለት ቀን ጊዜ ውስጥ እንኳን ብዙ ሊገቡኝ ያልቻሉ ነገሮች ተፈጽመዋል " ለመሆኑ አባቴ ካንተም ገንዘብ ወስዶብህ ነበር?

« የለም እሳቸው ከኔ ገንዘብ ተበድረው አያውቁም ። »

« አሁን አንተ ኢስት ሊንን ግዝተኸዋል " የራሴም ሁኔታ ምን እንዶሚመስል እየታየኝ ነው» አለችው ወዲያው ዕንባዋ በዐይኖችዋ ሞላ « መቸም ራሴን መደገፍ እስካልቻልኩ ድረስ በመጠጊያ ረገድ አንተን ማስቸገሬ አይቀርም »

« ሳቤላ . . . ምንም ዐይነት ሰቀቀን ሳይሰማሽ እስከ ፈለግሽበት ድረስ መቀመጥ ትችያለሽ »

« እግዚአብሔር ይስጥልኝ » ለጥቂት ቀኖች ነው " ምን ማድረግ እንዳለብኝ
እስካስብ ድረስ ከዚህ እሰነብታለሁ " ለመሆኑ ሚስተር ካርላይል ... ያባቴ ዕዳ
ትናንት የሰማነውን ያህል ይመስልሃል የተረፈ ገንዘብ አይኖረውም ? »
#የጣሪያ_ስር_አበቦች


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ


ሰዓታት የሚመስሉ ደቂቃዎት

ሁሉም ቀኖች በአንድ ዓይነት አለፉ

ጊዜን ተትረፍርፎ ስታገኙት ምን ትሰሩበታላችሁ? ሁሉንም ነገሮች አይታችሁ ከጨረሳችሁ አይኖቻችሁን ምን ላይ ታሳርፋላችሁ? የቀን ህልሞች ወደ ባሰ ችግር ሊመሯችሁ የሚችሉ ከሆነ፣ ሀሳቦቻችሁ የትኛውን አቅጣጫ ሊይዙ ይገባል? ውጪ ስሮጥ፣ ጫካ ውስጥ ለመጫወት ነፃ ስሆን፣ የደረቁ ቅጠሎች
እግሬ ስር ሲንኮሻኮሹ አስባለሁ በአቅራቢያ ባለው ሀይቅ ውስጥ መዋኘትን አልማለሁ፤ ወይም በቀዝቃዛ የተራራ ምንጭ ውስጥ ስለ መንቦራጨቅ አሰላስላለሁ። ነገር ግን የቀን ህልሞች ወደ እውነታው በተመለሱ ጊዜ ልክ
እንደሸረሪት ድር በቀላሉ የሚቀደዱ ናቸው። ደስታዬ የት ነው? ትናንትናዎች ውስጥ? ነገዎች ውስጥ? በዚህ ሰዓት፣ በዚህ ደቂቃና በዚህ ሰኮንድ አይደለም? የደስታ ፍንጣቂ የሚሰጠን አንድ ነገር አለ፣ አንድ ነገር ብቻ እሱም ተስፋ ነው።

ክሪስ ጊዜ ማባከን ከባድ ወንጀል ነው ይላል ጊዜ ዋጋ አለው ማንም በቂ ጊዜ የለውም ወይም በበቂ ሁኔታ ለመማር በቂ ጊዜ አይኖርም ዓለም ወደ እሳት እየሄች እንዳለች ሁሉ “ፍጠኑ! ፍጠኑ!” የሚል ጩኸት ሞልቷል።
እኛ ግን የምናባክነው ጊዜ፣ የማንሞላው ሰዓት፣ የምናነባቸው በሚሊየን የሚቆጠሩ መፃህፍት፣ ሀሳቦቻችንን ክንፍ የሚያስወጣ ጊዜ አለን፡ መፍጠር የሚችል አዋቂ ሰው የሚጀምረው ዝም ብሎ ከመቀመጥ ቅፅበት ነው
የማይቻለውን በማለም ከዚያ እውነት እንዲሆን ያደርገዋል።
እናታችን ቃል እንደገባችው ልታየን መጣች ሰዓታችንን የሚይዙልን
አዳዲስ መጫዎቻዎችና አሻንጉሊቶች ተሸክማ ነበር። ለመንትዮቹ ግን ህግ
ያለበት ጨዋታ ለመጫወት እድሜያቸው ስላልደረሰ ከባድ ነበር፡ ምንም ነገር ፍላጎታቸውን ይዞ አይቆይም እናታችን ካመጣቻቸው ብዙ ትንንሽ
መጫዎቻዎች ውስጥ በአልጋዎቹ ስርና በልብስ ማስቀመጫው ላይ የሚሄዱ የኤሌክትሪክ ባቡሮችና ገልባጭ መኪናዎችም ነበሩበት የሆነ ብንለውጠውም እንኳን መንትዮቹ ጣሪያው ስር ያለውን ክፍል ሁሉ ነገሩን ጠልተውት ስለነበር ይህንን በማግኘታቸው አስደሳች ሆነላቸው።

ጮሆ የሚቀሰቅስ ሰዓት የለንም: ያለን የእጅ ሰዓት ብቻ ነው፡ ቢሆንም ግን በየቀኑ በጠዋት እንነሳለን፡ እኔማ ብፈልግም እንኳን በሰውነቴ ውስጥ ያለው
አውቶማቲክ የጊዜ መቁጠሪያ አርፍጄ እንድተኛ አይፈቅድልኝም

ከአልጋችን ስንነሳ ሁሌም ወንዶቹ ቀድመው መታጠቢያ ክፍሉን ይጠቀማሉ። ቀጥሎ ኬሪና እኔ እንገባለን አያትየው ከመግባቷ በፊት ልብሳችንን ለብሰን መጨረስ አለብን፡ ከዚያ... አያትየው ወደ አስቀያሚው ደብዛዛ ክፍል ትገባና የያዘችውን የሽርሽር ቅርጫት አስቀምጣ እስክትሄድ ድረስ በተጠንቀቅ እንጠብቃለን አልፎ አልፎ ታናግረናለች። የምታናግረንም ምግብ ከመብላታችንና ከመተኛታችን በፊት መፀለያችንንና ትናንት ከመፅሀፍ ቅዱስ
አንድ ገፅ ማንበባችንን ለመጠየቅ ብቻ ነው:

“አይ” አለ ክሪስ አንድ ማለዳ፤ “ያነበብነው አንድ ገፅ ሳይሆን ብዙ ምዕራፎችን ነው " አለ። መፅሀፍ ቅዱስን የምታነቡት በቅጣት መልክ ከሆነ፣ ብትተውት
ይሻላል እኛ አስደናቂ ምንባብ ሆኖ ነው ያገኘነው: ካየናቸው ፊልሞች በላይ ስለደምና ስለ ወሲባዊ ነገር የሚናገር መፅሀፍ ነው: ካነበብናቸው ሌሎች መፅሀፍት በላይ አብዝቶ ስለ ኃጢአት የሚናገር መፅሀፍ ነው

“ዝጋ አንተ ልጅ!” ጮኸችበት: “የጠየቅኩት እህትህን እንጂ አንተን አይደለም"

ቀጥሎ ከመፅሀፍ ቅዱስ ያጠናሁትን አንድ ጥቅስ እንድነግራት ጠየቀችኝ።
አብዛኛውን ጊዜ በዚህ መንገድ በእሷ ኪሳራ ቀልዶች እንፈጥራለን᎓ ምክንያቱም በደንብ ካያችሁትና ረጅም ጊዜ ከፈለጋችሁ፣ ከመፅሀፍ ውስጥ የትኛውንም
ሁኔታ የሚመጥኑ ቃላት ታገኛላችሁ በዚህ ማለዳ መልስ ስሰጥ “በመልካሙ ፋንታ ለምን ክፉን መለሳችሁ?” ዘፍ 444 አልኳት።

ፊቷን አጨፈገገችና ዞራ ሄደች። ክሪስ ላይ ከመጮኋ በፊት ሌሎች ጥቂት ቀናት አለፉ፡ መንገዱን ሳታይና ጀርባዋን እንዳዞረች “ከኢዮብ መፅሀፍ ውስጥ
ያጠናኸውን ጥቅስ ንገረኝ፡ መፅሀፍ ቅዱስ ሳታነብ
እንዳነበብክ አድርገህ
ልታሳምነኝና ልታሞኘኝ እንዳትሞክር” አለችው:

ክሪስ በደንብ የተዘጋጀና በራሱ የሚተማመን ይመስላል፡ ኢዮብ 2812 ነገር ግን ጥበብ የምትገኘው ወዴት ነው? የማስተዋልስ ስፍራ ወዴት ነው
ኢዮብ 2828 “እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብ ነው፤ ከኃጢአትም መራቅ ማስተዋል ነው" ኢዮብ 31፡35 “የሚያዳምጠኝ ምነው በኖረልኝ እነሆ የእጅ ምልክት ሁሉን የሚችል አምላክ ይመልስልኝ፡” ኢዮብ 32፡1 “በዕድሜ ያረጁ
ጠቢባን አይደሉም: ያለማቋረጥ እየቀጠለ ነበር። ነገር ግን የአያትየው ፊት በቁጣ ቀለሙን ቀየረ ከዚያ በኋላ ክሪስን ከመፅሀፍ ቅዱስ ያነበበውን ጥቅስ እንዲነግራት ጠይቃው አታውቅም: በመጨረሻ እኔንም መጠየቅ አቆመች::
ምክንያቱም እኔም ሁልጊዜ የምነግራት የሚያናድዷትን ጥቅሶች ነበር:

ሁልጊዜ ምሽት አስራ ሁለት ሰዓት ገደማ እናታችን እያለከለከች በችኮላ ትመጣለች: ስጦታዎች፣ የምንሰራቸው አዳዲስ ነገሮች ፣ የምናነባቸው አዳዲስ መፃህፍት፣ የምንጫወታቸውን አዳዲስ ጨዋታዎች ተሽክማ ትመጣለች: ከዚያ ሰውነቷን ለመታጠብና ምድር ቤት ለሚዘጋጀው የራት
ግብዣ የሚመጥን ልብስ ለመልበስ ፈጥና ትመለሳለች ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለ እንደምትነግረን ከሆነ አሽከሮችና ገረዶች በጠረጴዛው አጠገብ
ቆመው በሚጠብቁበት ግብዣ ላይ፣ አብዛኛውን ጊዜ እንግዶች አብረዋቸው ይመገባሉ፡ “ትልልቅ የስራ ስምምነቶች የሚከናወኑት በምሳ ውስጥ ወይም በእራት ጠረጴዛ ላይ ነው'' ተብሎ ተነግሮናል።

ከጥቂት ደቂቃዎች የበለጠ ጊዜ አብራን የምታሳልፈው ቅዳሜና እሁድ ብቻ ነው ትንሽዋ ጠረጴዛችን ላይ ለምሳ አብራን ትቀመጣለች። ሆዷን መታ መታ እያደረገች “ከአባቴ ጋር ምሳ ከበላሁ በኋላ እንደገና ከልጆቼ ጋር ለመብላት ስል መተኛት እፈልጋለሁ ብዬ ነው ወደዚህ የምመጣው: እንዴት
እንደወፈርኩ ተመልከቱ” ትለናለች።

ከእናታችን ጋር መመገብ ከአባታችን ጋር የነበረውን የድሮውን ጊዜ ስለሚያስታውሰኝ ደስ የሚል ነበር። አንድ ቅዳሜ እናታችን ገና ውጪ ሆና
ሽታው የሚጣራ የቫኒላ አይስክሬምና የቸኮሌት ኬክ ይዛ መጣች: አይስክሬሙ ቀልጦ ሾርባ መስሏል ግን በላነው ምሽቱን አብራን እንድትቆይና በኬሪና
በእኔ መካከል ተኝታ ጠዋት ስንነቃ አጠገባችን መሆኗን ማየት እንድንችል ለመንናት: ምስቅልቅል ያለውን መኝታ ቤት ዙሪያውን ተመለከተችና ጭንቅላቷ ነቀነቀች “አዝናለሁ አልችልም በፍፁም አልችልም: ሠራተኞቹ አልጋዬ ለምን እንዳልተተኛበት ይጠራጠራሉ ይሄኛው አልጋ ደግሞ ይጠብባል አለችን።

“እማዬ፣ ለምን ያህል ጊዜ ነው? ሁለት ሳምንት ሆኖናል ግን ልክ ሁለት አመት ያህል ነው የሚመስለው: አያታችን አባቴን በማግባትሽ አሁንም ይቅር አላለሽም? አሁንም ስለኛ አልነገርሽውም?” ብዬ ጠየቅኳት

የማይጨበጥ አድርጌ በቆጠርኩት አነጋገር “አባቴ አንደኛውን መኪናውን
እንድነዳው ሰጥቶኛል፡ ይቅርታ እንደሚያደርግልኝ አምናለሁ ባይሆን ኖሮ መኪናውን እንድጠቀም ወይም አብሬው እንድኖር ወይም የእሱን ምግብ
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አስራ_ሶስት

///
እንደተለመደው ከሳምንት በኃላ ወደሆቴል መጥታ እኔም ስራዬን ስሰራ አሷም ስትዝናን አምሽተን እኩለ ለሊት ላይ ተያይዘን ወደተከራየችው ሆቴል በመግባት ተቃቅፈን ተኝተን እያወራን ነው፡፡እንዴት እንደሆነ አለወቅም ወሬው ደግሞ እንደወትሮው  ፍቅር ፍቅር ሚሸት ሳይሆን ኮምጠጥ ያለ ሀገራዊ ጉዳይ ነው..፡፡ዛሬ እንኳን እሷን የሚመጥናትን ጫወታ ልጫወት ብዬ መሰለኝ በገዛ ጥያቄዬ ውስብስብ ወሬ ውስጥ እነንድንገባ መንገዱን የከፈትኩት

‹‹መቼስ ወታደር ነሽ…ለዛውም ባለትልቅ ማአረግ….የሀገሪቱን ችግር  ለማከምና ከመከራዋ እንድትወጣ ለማገዝ በደምና በላብ ዋጋ ከፍለሻል…ግን አሁን ስታስቢው መስዋዕትነቴ ባክኗል….ደሜም ያለውጤት ፈሷል ብለሽ ታስቢያለሽ፡፡?››ስል ጠየቅኳት፡፡

እስኪ ምን ሚሉት ጥያቄ ነወ….ይሄንን ጥያቄ አንድን የተከበረች ጄኔራል ስጠይቅ የሀገሪቱ ደህንንት ቢሮ ጆሮ ቢገባ የትኛው ተቃዋሚ አካል ነው አስርጎ ያስገባህ ብሎ  ቢያፍነኝ  ይፈረድበታል?
እሷ ግን ተረጋግታ መመለስ ጀመረች‹‹ፈፅሞ አላስብም…አርግጥ እኔ እንዲሆን እያሰብኩና እያለምኩ እንደነበረው የተከወነ ነገር ላይኖር ይችላል፡፡ውጤቱ ከግምቴ በጣም ዝቅ ያለ ወይንም ሙሉ በሙሉ ተቃራኒ ሊሆን ይችላል…እንደዛም ነው የሆነው፡፡ግን እኔ ነገሮችን ለማስተካከል በተሰጠኝ  ኃላፊነትና ሪሶርስ በአግባቡ በመጠቀም በቀናነት እናም በሙሉ ችሎታዬ ተንቀሳቅሼለሁ ወይ ?ብዬ ነው የምጠይቀው…መልሱ አዎ ከሆነ በቂ ነው፡

ነገሮችን ሁሉ በውጤታቸው ብቻ ከለካህ መጨረሻው ጥሩ አይሆንም… ወደፊትም አያስኬድህም፡፡
‹‹እስቲ አብራሪልኝ››
‹‹ስራዎችን ከመከወንህ በፊት ስለስራው ሞያዊ ጥናት   ታርጋለህ፡ ውጤታማ የሚደርግህን እቅድ ትነድፋለህ ፡ከዛ ወደተግባር ትገባለህ…. .በእኔ አረዳድ እቅድ በወረቀት በሰፈረው መሰረት ተግባራዊ የሚሆነው ከ50 ፐርሰንት በታች ነው..ማንኛውም እቅድ ማለቴ ነው..የጦርነት እቅድ ሲሆን ደግሞ የተለየ ይሆናል….ግን ደግሞ  እቅድ አስፈላጊና በጥንቃቄ መሰራት የሚገባው ጉዳይ ነው..ቢያንስ ነገሮችን ለመጀመር መነሻ ይሆንሀል፡: በሂደት ለሚያጋጥሙህ እዲስ ክስተቶች የሚሆን የሚሳራ ቅፅበታዊ እቅደም ለማቀድ  መነሻ  ፍንጭ ይሰጥሀል…በአጠቃላይ ለማለት የፈለኩት እንኳን እንደኛ የተወሳሰበና የተጨመላለቀ የችግር ትብታብ ያለባት ሀገር ይቅርና ባደጉት ሀገሮች የማስፈፀም ብቃት እንኳን ነገሮች እንደሀሳብ አይሄዱም..ምሳሌ አሜሪካ ኢራቅን ሰትወር  የስንት ቀን ኦፕሬሽን ብላ ገባች? ስንት አመትስ ፈጀባት…?ራሺያ ዩክሬንን ላይ ለሳምንት ብላ የጀመረችው ጦርነት  ምን ያህል ጊዜ ፈጀባት ?
ይሄ የወታደራዊ ፤ አመራሩ ችግር፤የፖለቲካኛው ችግር ፤የቦታው ነባራዊ ሁኔታ..የተፋላሚህ አቅድህን ለማበላሸት  የሚነድፈው ሌላ እቅድ…የተፋላሚህ ወዳጆች ተፅዕኖ፤የአንተ ጠላቶች በሁኔታው ለመጠቀም የሚያደርጉት ጥረት፤ ጠላትም ወዳጅም ሳይሉ ከነገሩ ገቢያቸውን ለማደለብ የሚዳክሩ ሚዲያዎች፤ነጋዴዎች፤ ደላላዎች….ምኑ ቅጡ…የአንተ ዕቅድ በእግዚያሄር ካልተዘጋጀ በስተቀር የእንዚህን ሁሉ ተዋናይ ትርምስ ከግምት አስገብቶና   በትክክል ተንብዮ የሚሰራ እቅድ ሊያዘጋጅልህ አይችልም…..እና መጀመሪያ        ይሆናል ተብሎ ተነገሮህ አንተም ያንን አምነህ ወደጦርነት ትገባለህ..እንዳልከው ላብህም ይንጠባጠባል ፤ ደምህም ይረጫል  …አካልህም እየተቦደደሰ ይበራል…..ነፍስህም ልትሰናበት ችላለች…. ውጤቱ ደግሞ ከታሰበው ተቃራኒ ወይንም በጎን የልታሰበ ሽንቁር ከፍተት እየተስገመገመ ወዳልታወቀ መዳረሻ የሚያደርስ ሊሆን ይችላል፡፡

፤የዛን ጊዜ  ልትደነግጥ ትችላለህ…ሊከፋህ ይችላል…ግን በምንም አይነት ተስፋ አትቆርጥም…ተስፋ መቆረጥ ከሁሉም ጠባሳዎችህ እንዳታገግም እና ሁለተኛ እድል እንዳሞክር እስከወዲያኛው ነው የሚያደቅህ….ሀገር ደግሞ ቢያንስ ህልውናዋ ማስጠበቅ የምትችለው ሁል ጊዜ ተስፋ በማድረግና ከነመዝረክረኩም ቢሆን ወደፊት በመጎዝ ነው፡፡በምንም አይነት ሁኔታ በሀገርህ ላይ ያለህ ተስፋ በውስጥህ እንዲፈርስ ልትፈቅድ አይገባም፡፡በተለይ በዚህ የኢንፎርሜሽን ዘመን ጦርነት በጣም የማይተነበይ እና የሸረሪት ድር አይነት የተወሳሰበ ሆኗል፡፡

ከሌላ አካል ተልኮ ተሰጥቶት እንደሚጠይቅ እንደ ችኮ ጋዜጠኛ ሙግቴን ቀጠልኩ‹‹ግን የእኛ ሀገር ዋና ችግር ምን ይመስልሻል…?ድህነታችን መሆኑን አውቃለሁ…. ቢሆንም እንደወታደር በሀገሪቱ ፍፅም ሰለም እንዳትሆን ዋናው እንቅፋት ምንድነው?፡፡

‹‹ትክክል ነህ እኮ.. በግራም ዞርክ በቀኝ ለእኛ ሀገር ዋነው ችግራችን ድህነታችን ነው፡፡፡ሚያናጥቀንም ሚያላትመንም እሱ ነው፡፡ግን ከድህታችን በመለስ ዋናው ችግር ምንድነው ካልከኝ ፅንፈኝነት ነው…ፅንፈኝነት ማለት አይነ ልቦናል ጨፍኖ በደመነፍስ ማሰብ ነው፡፡ያ ማለት በውድቅት ለሊት የቤቱን መብራት ሁሉ አጥፍቶ የጠፋብንን መርፌ ለማግኘት የመዳከር ያህል ነው፡፡ቀንቶህ መርፌውን በዳበሳ መጨበጥ ብትችል እንኳን መወጋትህና መድማትህ አይቀርም፡፡
ፅንፈኝነት የራስን ፍላጎት ጥቅምና ስሜት ብቻ  መሰረት አድርጎ ብይን መስጠት ለዛም ብይን  ደምሳሽና ጨፍላቂ ውሳኔን መውሰድ ማለት ነው፡፡

አክራሪነት በብዙ    ዘርፍ አለ....የብሄር አክራሪነት፤ የሀይማኖት አክራሪነት ፤የፆታ አክራሪነት ፤የፖለቲካ አክራሪነት…የሀገር አክራሪነት ወዘተ፡፡ፅንፈኝነት ነገሮችን ከአንድ የተቸነከረ ፖይንት ኦፍ ቪው ብቻ መመልከትና ፍርድ መስጠት ማለት ነው፡፡ወደአንዱ ፅንፍ በጣም ተለጥፈን ስንቆም ከሌላኛው ፅንፍ ያለን ርቀት በጣም ሰፊ ይሆናል…ከእይታችንም ይጠፋል፡፡
ፅንፈኞች መቼም የእኛ ነገር የመጀመሪያው ይሁን…የእኛ ነገር ይሰማ …የእኛ ነገር ይቀመስ ፤ የእኛ ነገር ይበላ….ባይ ናቸው፡፡ማመቻመች የሚባል ነገር ፈፅሞ አልፈጠረባቸውም…. የጋራ በሆነ ነገር ላይ ደግሞ የእኔ ብቻ አይሰራም…፡፡
እና እንደአንድ ወታደር የትኛውንም ሀይማኖት ተከታይ ብትሆን ችግር የለብኝም.፤የየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ብትሆን እኔን አይመለከተኝም…አህዳዊ ብትሆንም ፌዴራሊስት ብትሆንም ግድ አይሰጠኝም….ግን ሁሉም ውስጥ ሆነህ ፅንፈኛ ከሆንክ የዛን ጊዜ ችግር አለ..አንዳንድ ሰው አክራሪነት ላይ የተሳሳተ የትርጉም ስህተት ሲፈፅም አያለሁ….አንድ ሰው የራሱን ሀይማኖት ይዞ የሀይማቱን ዶግማዊና ቅኖናዊ ህግጋን ሳያፋለስ በፍፅም መሰጠትና ትኩረት ተግባራዊ በማድረጉ አክራሪ ሀይማተኛ ነው ልንለው እንችላለን…አክራሪነቱ ግን የሌላው ሀይማኖት አማኝ ላይ ድንጋይ እስካልወረወረ እና የሌላውን አማኝ ማምለኪ ቦታ ላጥቃና ላውድም እስካላለ ድረሰ በክፍትም በስህተትም ሊወሰድ አይገባም….፡፡በብሄርም ስትመጣ እንደዛው…አንድ የኦሮሞ ብሄር ተከታይ በኦሮሚኛ ቋንቋ ማውራቱ..በእየእለቱ የኦሮሞ ባላዊ ልብስ መልበሱና ገንፎና፤አንጮቴ እና ወተት የእየለት ምግቡ ማድረጉ በፍፅም ችግር የለውም…..ችግሩ በአካባቢዬ ያለው ስው ሁሉ ከአንጮቴ ውጭ ሌላ ምግብ እንዳይቀምስ ካለና በጆሮዬ ከኦሮምኛ ውጭ ሌላ ቋንቋ አንዳይሰማ በማለት  ከሌላው ብሄር ጋር ባለው መስተጋብር ችግር መፍጠር ከጀመረ ነው፡፡
#ባል_አስይዞ_ቁማር


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ከአስር ጊዜ በላይ ደውሎላት ነበር ቀልቧ ቃል ላይ ተለጥፎ ስለነበረ አላነሳችለትም ..እና አሁን ለዛ ነው እየደወለችለት ያለችው፡፡
አነሳላት‹‹‹ምነው አንቺ ይሄን ሁሉ ስደውል?››
‹‹አላየሁትም ነበር..ስልኬን መኝታ ቤት ጥዬ ሳሎን ነበርኩ….››
‹‹ምን አስዋሸሽ ማሚ ጋር ደውዬ መኝታ ቤትሽ እንደሆንሽ ነግራኛለች፡፡››
‹‹አይ አንተ ሰው..ስለእኔ ዘበኞችንም ቤት ሰራተኞችንም እናቴንም መጠየቅ አይደክምህም?››
‹‹እንደዛ እንዳላደርግ ከፈለግሽ ስፈልግሽ ተገኚያ››
‹‹እሺ……››
‹‹በቃ ለንቦጭሽን አትጣይ..ንፍቅ ብለሺኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹እንዴ ጥዋት እኮ አብረን ነበርን››አለችው…ስልክ ስላላነሳችለት ብቻ እንዲህ መንጨርጨሩ አስገርሞታል…ምን ስታደርግና ምን ስታስብ የእሱን ስልክ እንዳላነሳች እውነቱን ቢያውቅማ ጨርቁን እንደሚጥል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹እኔ እኮ እንደአንቺ ደንዳና ልብ የለኝም…ለሰከንድም ባትለይኝ ደስ ይለኛል… በጣም እኮ ነው የማፈቅርሽ››
‹‹እኔም አፈቅርሀለሁ››ለምን እንደሆን ባታውቅም ይሄን ቃል ምን አልባት ከሺ ጊዜ በላይ ለእሱ ተጠቅማለች፡፡ከልቧ ደስ ብሏትና የእውነቷን ነበር ቃሉን ከአንደበቷ የምታወጣው….፡፡ዛሬ ግን ከበዳት ….እየሻከረት ነው የተናገረችው፡፡
‹‹…ፍቅርን እያቆሸሽኩት ይሆን እንዴ?…..ቺት እያደረኩብት ይሆን እንዴ…?ምን ያደረኩት ነገር አለ….? ተጀናጀንኩ.. ተሳሳምኩ..ምን ፈፀምኩ….?›› ብላ እራሷን ለማፅናናት ብትሞክርም ልቧ ግን ለሆነ ሌላ ሰው መቅለጥ መጀመሯን መዋሸት አልቻለችም…፡፡
ከእዚህ ጉድ ለመውጣት ቶሎ ይሄን ሰው ማግባት እንዳለባት ቅፅበታዊ ውሳኔ ወሰነች ‹‹…ልዩ ሳትወራጂ ይሄን ነገር አድርጊው››እራሷን መከረች…እና ወዲያውኑ ወደተግባር ተሸጋገረች፡፡
‹‹ስማ…›
‹‹ወዬ የእኔ ፍቅር…››
‹‹ደግሞ ሸጉጠሀኝ ውለህ ሸጉጠኸኝ ማደር ከፈለክ ጠቅልሎ ማግባት ነዋ…››
‹‹ምን?››
‹‹አዎ ሰምተሀል…››
‹‹መለመን ከጀመሪኩ እኮ አመት ሊያልፈኝ ነው…አንቺ ነሽ ሰበብ እየፈጠርሽ ስታዘገይው የነበረ፡፡››
‹‹ለትምህርቴ ብዬ ነዋ..አሁን ደግሞ ለምርቃት ሶስት ወር ነው የቀረኝ፡፡››
‹‹አንቺ የሆነ ሀሳብ መጣልኝ..፡፡››
‹‹ምንድነው ?ልስማው…››
‹‹ለምን አንድ ቀን አናረገውም…?ማለቴ አንድ ቀን እንኳን ባይሆን ተከታታይ ቀን ይሁን..፡፡ ››
‹‹አይ አንደዛ አይሆንም.. ሁለቱንም ለየብቻ ነው ማጣጣም የምፈልገው… ግን ምርቃቴንና ቀለበቴን በአንድ ቀን ማድረግ እንችላለን፡፡
‹‹አሪፍ ነው…ግን ቀለበት አስሮ ብቻ አንድ ቤት መግባት ይቻላል እንዴ?››
‹‹አዝናለሁ እንደዛ አይቻልም፡፡››
‹‹ወይ ታዲያ ምንድነው ትርፌ?››
‹‹በወሩ ደግሞ ሰርግ ይሆናላ…››
‹‹ምሽቱን ሙሉ ስታበሳጪኝ ያመሸሽው እንዲህ አይነት የሚያስፈነጥዝ ዜና ልታሰሚኝ ነው…..በስመአብ ….በጣም ነው የማፈቅርሽ..››
‹‹እኔም አፈቅርሀለሁ..በል ደህና እደር..፡፡››
‹‹ደህና እደሪ …ደግሞ ነገ አላልኩም እንዳትይ….ንግግራችንን ቀድቼዋለሁ››
‹‹የሰው ድምፅ ያለፍቃድ መቅዳት ወንጀል እኮ ነው፡፡››
‹‹የሰው ድምፅ አልቀዳሁም ፤የሚስቴን ነው…የሚስቴ ድምፅ ማለት ደግሞ የራሴ ነው፡፡››
‹‹በል ይሁንልህ… ቻው፡፡›
‹‹ቻው››
ስልኩን ዘጋችና በድንጋጤ ጭንቅላቷን ያዘች‹‹…ልዩ ምድነው የሰራሽው…? አሁን ከአራት ወር በኋላ ሚስትና የቤት አስተዳዳሪ ለመሆን ዝግጁ ነሽ……?ልጅ ወልደሽስ ማሳደግ ትችያለሽ…?.›› እራሷን አምርራ ብትወቅስም አንዴ ከአንደበቷ ያወጣችውን ቃላት ሰብስባ መልሳ ልትወጣቸው አልችለችም፡፡
‹‹….እስኪ ገና ለገና ፍቅር ከሌላ ሰው እንዳይዘኝ ተብሎ ያልሆነ መክለፍለፍ ውስጥ ይገባል…?››እራሷን አምርራ ወቀሰች፡፡
ከልጁ ፍቅር እንዳይዛት ቀላል ዘዴዎች ነበሩላት..ለምሳሌ እቤቱ አለመሄድ… መኝታ ቤቱ የቀበረችውን መከታተያ እንዳይሰራ ማበላሸት…ስልኩን ከስልኳ ላይ ማጥፋት…በቃ ካልደወለችለት እንደማይደውልላት እርግጠኛ ነች..እቤቱ ካልሄደች እሱ እቤቷ አይመጣም…ጭራሽ አድራሻውንም አያውቀውም…ታዲያ ከእሱ ፍቅር እንዳይዛት ልትወስድ ያሰበችው እርምጃ ምን የሚሉት ነው .. በቅፅበታዊ ውሳኔዋ እራሷን ጠላች …
ግን ፍቅር እንዳይዘኝ እንዳይዘኝ የምትለው እስከአሁን አልያዘትም ማለት ነው…..?ፍቅር ያዘት ተብሎ በእርግጠኝነት የሚወራው የፍቅሩ መጠን ምን ያህል ሲሆን ነው? መለኪያውስ ምንድነው?ይህንን እሷስ ታውቀዋለች?
እና ደግሞ አሁን በዚህ ሰአት ቃል ከተኛበት ተነስቶ ከራሷ ኮሚፒተር እሱ ቤት በደበቀችውን ካሜራ ሀክ አድርጎ እሱን መኝታ ቤቱ የሚያደርገውን እያየች እያሳየች የነበረውን ስሜት መድሀኔ ጋር ደውላ ስለመጋባት የተነጋገረችውን ስልኩን ከዘጋች በኃላ በተናገረችው ተፀፅታ ስትቆጭ ጠቅላላ ቆይታዋን ሰምቶ ተገርሞ መልሶ እንደተኛ ብታውቅ ምን ትል ይሆን?

ይቀጥላል
#ተአምራተ_ኬድሮን


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///

የድባአለ አባትንና አዲሱ ሚስቱ ግን ከለሌቱ ስምንት ሰዓት  አልጋቸውን ለቀው ወርደው የቤቱ ወለል ላይ ጎን ለጎን በላብ እንደተዘፈቁ ቁጭ ብለው በመነጋገር በጥዋት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚለያዩና ሰውዬውም ወደሚስቱ መመለስ እንዳለበት ወስነው ነበር እዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሱት… ኬድሮን ማታ ባስፈራራቻቸው ላይ ተመስርተው ብቻ ሳይሆን እሷ እንዳለችው ሁለቱም ባዩት ህልም የተነሳ ነው..የሚገርመው ደግሞ ሁለቱም ያዩት ህልም በጣም አስፈሪ እና ሰቅጣጭ  መሆኑ ብቻ ሳይሆን ምንም ልዩነት የሌለው ከመጀመሪያው እሰከመዝጊያው ተመሳሳይና አንድ አይነት በመሆኑ ነው፡፡

ጥዋት ሁለት ሰዓት ሳይሞላ ይዞ የወጣውን ሻንጣ እንዳንጠለጠለ ወደቀድሞ ቤቱ ተመልሶ ሚስቱ እግር ስር ተደፋ፤እሷም ሆነች ልጆቹ በእልልታ ተቀበሉት….ኬድሮምም ወደተለመደ እረኝነቷ  ከመሄዷ  በፊት ከድባለ  እናት  እቃ የገዙት የጎረቤት ሴቶች ጋር በየቤታቸው  በመዞር.. ሰውየው ስለተመለሰ የገዛችሁትን እቃ በስጦታ መልክ መልሳችሁ እንደምታስደስቷት አምናለሁ›› በማለት በአዋጅ መልክ ለሁሉም በመናገር ነበር ወደሰራዋ የተሰማራችው...እንዳላቸውም ማታ ስትመለስ ሁለት ጅግራ እንደተሸከመች እነከድር  ቤት ስትደርስ እቤቱ ትናንት ከነበረው በተቃራኒው በደስታ ደምቆና በሳቅ ፍክቶ ነበር የጠበቃት..
ደጃፉን አልፋ‹‹ ቤቶች›› የሚል ድምፅ እንዳሰማች ነበር.ከድር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመብር የተጠመጠመባት እናትየውም በደስታና በስስት አቅፋ እየወዘወዘቻት ሞጨሞጨቻት ..ከዛ ቤቱ ሰላም መመለሱን አረጋግጣ…ከቤቱ የተሸጡ እቃ አንድም ሳይቀር መመለሱን አይታ ጀግራውን ለደስታቸው ማድመቂያ ይሆን ዘንድ አስረክባ ወደቤቷ ስትመለስ  ድባለ  ከኃላዋ ተከትሎ አስቆማት

‹‹እሺ አሁን ደግሞ ምን ፈለክ?››

‹‹አንድ ነገር ልነግርሽ ነው››

‹‹እኮ ቶሎ ንገረኝና ወደቤቴ ልግባበት››

‹‹ሳድግ  አገባሻለሁ፡፡››

‹‹ማግባት ማለት? አንደዚህ እንደአባትህና እናትህ?››

‹‹አዎ ምነው?››

‹‹ቲሽ ምነው ትላለህ እንዴ…?››

‹‹ልጇች አስታቅፈኸኝ ..ሌላ ሴት ልታገባ››

‹‹አረ እንደዛ አላደርግም አንቺን እኮ በጠም ፈራሻለሁ››

‹‹በል እርሳው .እኔ ባል መቼም አለገባም››

‹‹ቻው በቃ ..እኔም ሚስት አላገባም››ብሎ አንገቱን በመድፋት ፊቱን አዙሮ ወደቤቴ ተመለሰ…

እሷም እያጉረመረመች ወደቤቱ እርምጃዋን ቀጠለች፡፡በዛ ዕድሜዋ እኚንና መስል እንደታአምር ሚነገሩ ድርጊቶችን መከወን የዘወትር ተግባሯ ነው፡፡እርግጥ ያው ተደጋግሞ እንደተነገረው እድሜዋና የሰውነቷ እድገት ተመጣጣኝ አልነበረም..ከእኩዬቾ በጣም የገዘፈችና የጠነከረች…ገና በአስር አመቷ ከሩቅ ታይተው ሚለዩ ጡቶች ያጎጠጎጠች..መቀመጫዋ ወደኃላ መግፋትና መንቀጥቀጥ የጀመረ በትክክል ሰትወለድ በአካባቢወ ኖሮ የሚያውቅ ሰው ካልሆነ በስተቀር ስለ ዕድሜዋ የሰማ ማንኛውም ሰው የማያመምነው አይነት ነው፡፡አሁን አብሯት ሲያወራ የነበረው ጓደኛዋ ዱባለ እንኳን  ድፍን ሁለት አመት ቢበልጣትም በማያጠራጥር  ሁኔታ ታላቁ የምትመስለው እሷ ነች፡
///

11 አመት ሲሞላት ወደ ትምህርት ቤት ተመለሰች፡፡ካርዷን ይዛ ሄደችና 3ተኛ ክፍል ተመዘገበች፤በሳምንት ሁለት ወይም ሶስት ቀን ብቻ ነው ክፍል ውስጥ ተገኝታ መምህራኑ የሚያስተምሩትን ትምህር የምትከታተለው፡፡ግን ደግሞ ያ የሚያመጣው ምንም አይነት ለውጥ የለውም…አንዱን የመማሪያ መፅሀፍ አንዴ ካነበች በኃላ  ፍፅም አትረሳውም… ሳምንቱን ሙሉ ክፍል ውስጥ መቀመጥ ለእሷ ብክነት ነው፡፡

13 ዓመት ላይ ሆና ነው፡፡የምትወዳት እናቷ ትታመምና ለተሻለ ህክምና ወደጎባ ሆስፒታል ሪፈር ተባላችና  እዛ ለአንድ ወር እንድትተኛ ይደረጋል፡በወቅቱ በታመመች ጊዜ ወደእዛ ይዟት የሄደው ታላቅ ወንድሟ ወይም የኬድሮን አጎት ነበር፡፡ከሳምንት ቆይታ በኃላ ግን ኬድሮን እናቴን ሄጄ ካለየሁ ሞቼ እገኛለሁ ትላለች…አረ ተይ እሷ እራሷ ሰሞኑን ስለሚሻላት ትመጣለች ብትባል ካላካችሁኝ ጠፍቼ ሄደለሁ በማለቷ ያው ካላቸው ልምድ ምንም ነገር አምርራ ከተናገረች እንደምታደረገው ስለሚያውቁ መሰፈሪያ ገንዘብ ሰጥተው ወደጎባ ከሚሄድ የጎረቤት ሰው ጋር በአደራ ሆስፒታል ድረስ ወስዶ ከእናቷ እና ከአጎቷ ጋር እንዲያገናኛት ይልኳታል፡፡በሰላም ትደርሳለች፡፡
አደራ የተቀበለውም ሰው እጇን ይዞ ሆስፒታል ድረስ በመውስድ ከእናቷና ከአጎቷ ጋር ያገናኛትና ወደራሱ ጉዳይ ይሄዳል…እዛ ሆስፒታል እናቷን እየተንከባከበችና አጎቷን እየገዘች አራት ቀን ያህል ከቆየች  በኃላ ግን ምንም እንኳን እናትዬው እየተሻላት ቢሆንም የጀመረችውን ህክምና እስክታጠናቅ ለተጨማሪ 10 ቀን መቆት አለባት ስለተባለ ከትምህርቷ ብዙ እንዳትስተጓጎል ይዟት የመጣው ሰውዬ ይዟት እንዲመለስ ይስማሙና በለሊት ከሰውዬው ጋር በአይሱዙ የጭነት መኪና አሰፍረው ይልኳታል፡፡

ደሎ መና ከጎባ ከተማ 110 ኪ.ሜትር ያህል የሚርቅ ቢሆንም መንገዱ ግን እጅግ በጣም አስቸጋሪ መልካአምድር ያለበት በተለየ ከጎባ አንስቶ እስከግማሽ ርቀት . ሪራ እስከተባለችው የገጠር ከተማ ድረስ ያለው መሬት በኢትዬጵያ ሁለተኛው ከፍተኛ ቦታ ባቱ ተራራ ሚገኝበት ከ4420 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ከፍታ ያለውና እጅግ ሚያንዘፈዝፍ ብርድ ያለበት በዛ ላይ እጅግ ጠመዝመዛ ገደልና ቁልቁለት እናም ደግሞ እንደእባብ ተጠማዞ በማያልቅ መንገድ  የተነጠፈበት ነው፡፡በአስፈሪው ወጣ ገባ መንገድ 50 ኪሎ ሜትር ያህል ከተጓዙ በኃላ ቀሪው ደግሞ ዝቅ እያለና በተነፃፃሪ የተሻለ የሚባል መንገድ  ሆኖ ግን ጥቅጥቅ ባለ ጫካና በአስፈሪ አውሬዎች የታጨቀ መንገድ በማቋረጥ ነው ደሎ ከተማ የሚገባው፡
ኬደሮን ከደሎ ወጥታ ሌላ ከተማ ስታይ ይሄ መጀመሪያ ገጠመኝ ነበር፡፡ትራንስፖርቱ አይሱዙ ጭነት መሆኑ በአካባበው የተመደ ትራንስፖርት ስለሆነ ነው፤ከመንገዱ አስቸጋሪነት የተነሳ ዋናው የትንስፖርት አይነቶች አይሱዙ ጭነት፤ኤፍ.ኤስ. አር ጭነት ፤ፒካፕ መኪና ሲሆን አልፎ አልፎ አይሱዙ ቅጥቅጥ ይገኛል...ከዛ ውጭ የተለመደው አይነት የህዝብ ማመላለሻ አውቶቢስና ሎንቺን፤ብሎም ሚኒባስ ያንን መንገድ አያስቡትም፡፡አይደለም እነሱ እራሳቸው የአይሱዙ ሹፌሮቹ ቢሆንም እያንዳንዱን የመንገዷን ወጣ ገባና  ኩርባ፤ ዝቅታና ከፍታ አብጠርጥረው የሚያውቁ ሰለሆነ ነው የሚወጡት.እዛ መንገድ ላይ ለመሾፈር ቅድሚያ በረደትነት አራትና አምስት አመት ቀጥቅጦ ማገልገልገልና የመኪናውን ብቻ ሳይሆን የመንገዱንም ፀባይ አብጠርጥሮ  ማወቅ የሚጠይቅ የጀግና ስራ ነው፡፡

ይቀጥላል
#ትንግርት


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ከትንግርት ጋር ከሀያ ቀናት በኃላ ነው በአካል የተገናኙት፡፡በጣም ናፍቃዋለች፡፡ ምግቡን እየበላ በመሀል ቀና እያለ ሸርፎ ይመለከታታል፡፡‹‹ቤት መዋል ስትጀምሪ ባለሞያ ወጥቶሻል፡፡›› አለ ሁሴን የቀረበለትን ምግብ በልቶ ጨርሶ እጁን እየታጠበ፡፡

የተበላበትን ዕቃ አነሳስታ ከጨረሠች በኋላ ለሁለቱም ተጨማሪ ቢራ ጠረጴዛ ላይ በማስቀመጥ ፊት ለፊቱ እየተቀመጠች፡፡‹‹ባክህ... በእጄ የተሠራውን ምግብ ለመቅመስ እድሉ ስላልገጠመህ እንጂ ድሮም ባለሙያ ነኝ፡፡ >> አለችው

‹‹መጠጥ አሁንም አልተውሽም ማለት ነው?››

‹‹መተው አልተውኩም... ግን በጣም ቀንሻለሁ፤ አንዳንዴ ሲያሠኘኝ ብቻ ነው ቀመስ የማደርገው››

‹‹ይህቺ ቀመስ እራስን መሸወጃ እንዳትሆን?››

‹‹አይመስልህ፤አልፎ አልፎ መጠጣቱ ያን ያህል መጥፎ መስሎ ስላልተሰማኝ ነው እንጂ ለማቆም ከብዶኝ አይደለም፡፡ ጫት፣ ሲጋራና አንተን በአንዴ እርግፍ አድርጌ መተው የቻልኩ ሠው እኮ ነኝ፡፡››

ሁሴን በንግግሯ ፈገግ አለና ንግግሩን ቀጠለ << እኔም ሱስሽ ነበርኩ ማለት ነው?ለዛውም ከጫትና ከሲጋራ እኩል ውስጥሽን የምጎዳ መጥፎ ሱስ? ለማንኛውም እፈልግሃለሁ ብለሽ ያስጠራሸኝ ለምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቻለሁ ?>>

‹‹ያን ያህል?››

‹‹ከምትገምቺው በላይ፡፡ አንቺን መፍራት ከጀመርኩ ሠነበትኩ እኮ፡፡ ነገረ ስራሽ ሁሉ ተዓምራዊ ነው፡፡ የዛሬው ደግሞ ምን እንደሆነ ልስማዋ!››

ከመቀመጫዋ ተነሳችና ወደ መኝታ ክፍሏ እየተውረገረገች ገባች፡፡ አተኩሮ ተመለከታት… ውበቷ ከቀድሞው በጣም የጨመረ መሰለው፡፡ አንዳንዴ የማያቃት አዲስ ሴት ትሆንበታለች፡፡ እርጋታዋ ያስፈራዋል፣ ብስለቷ ያስደነግጠዋል፡፡ በፊት ተሸፍነው የነበሩ ምርጥ ስብዕናዎቿ ዛሬ ጎልተውና አብበው መታየት ሲጀምሩ የማያውቃት ሴት መስላ ብትታየው ምኑ ይገርማል?፡፡

ተመልሳ መጣችና አንድ አበጥ ያለ እሽግ ካኪ ወረቀት አቀበለችውና ወደ መቀመጫዋ ተመልሳ ተቀመጠች፡፡

‹‹ምንድነው?›› ግራ በመጋባት ጠየቃት፡፡ዝም አለችው

‹‹ልክፈተው?›› መልሶ ጠየቃት፡፡

‹‹ምን አስቸኮለህ መጠጥህን ጨርሰህ ወደ ቤትህ ሄደህ ተረጋግተህ ታየዋለህ፡፡ ያን ያህል ጠቃሚ ጉዳይ አይደለም››አሁኑኑ ቤቱን ለቆ
ወጥቶ እሽጉን ለመክፈትና ውስጡ ያለውን ሚስጢር ምንነት ማወቅ ፈለገ፡፡ ደግሞም ስሜቱን እንደምንም ተቆጣጥሮ ሀሳቡን ቀየረ፡፡ ከእሷ አጠገብ መቀመጥ ከእሷ ጋር ማውራት ፈልጓል፡፡ አሁን ውድ ሆናበታለች፡፡ ሻይ ለመገባበዝ እንኳን እሷ በፈለገችና ባሰኛት ጊዜ እንጂ እሱ ሲፈልግ ሊያገኛት አይችልም፡፡ ስለዚህ ታግሶ ወደ ወሬው ተመለሠ፡፡

‹‹ያንን የጠየኩሽን ነገር ምን ወሠንሽ?›› ቢራውን ከነጠርሙሱ አንስቶ ተጎነጨና ጠየቃት፡፡

<<የቱን??>>

‹‹የሕይወት ታሪክሽን በጋዜጣዬ ላይ በተከታታይ አምድ ማሳተም እፈልጋለሁ ብዬሽ ነበር እኮ፡፡››

‹‹አስታውሳለሁ .. ግን አልወሰንኩም፡፡››

‹‹ብዙ ብር እኮ ነው የሚያስገኝልሽ .. የፈለግሽውን ያህል እከፍልሻለሁ››

የንዴት ፈገግታ ፈገግ አለች፡፡ ‹‹በቃ አንተ ከእኔ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ በብር ብቻ ነው ለመግዛት የምትጥረው፡፡ ፍቅሬን ወይንም ገላዬን በገንዘብ ስሸጥልህ ኖርኩ፤ዛሬም ታሪኬን በገንዘብ ልሽጥልህ?ያን ያህል አታውቀኝም ማለት ነው?››

ሁሴን ባላሠበው መንገድ ስለመጣችበት ተሸበረ፡፡ ትንግርት የሕይወቷን አቅጣጫ ከተቀየረ በኋላ ያስተዋለባት አንድ ለውጥ ይሄ ነው፡፡ በፊት ሲያውቃት ቻይ፣ሆደ ሠፊ፣ማንኛውን ንግግር የማያስከፋት፣ ቢያስከፋትም መከፋቷን ሳታሳውቅ በሳቅ ማሳለፍ የምትችል ብልህ ነበረች፡፡ አሁን ግን የተለየች ሆናለች::

‹‹እንደዛ ማለቴ አይደለም፡፡ ልዩ ታሪክ እንዳለሽ አምናለሁ፡፡ ይሄ ታሪክ ደግሞ ለተቀረው ማህበረሰብ አስተማሪ ስለሆነ ተዳፍኖ መቅረት የለበትም ብዬ ስለማስብ ነው፡፡ እስቲ እንዲታተም ባትፈቅጂ እንኳን ለራስሽ ፅፈሽ አስቀምጪው::››

‹‹ጽፌዋለሁ... በተለይ ባለፉት አምስት አመታት ያሳለፍኳቸውን በህይወቴ የተከሠቱ አንኳር ድርጊቶች በዲያሪዎቼ ላይ አስፍሬያቸዋለሁ፡፡››

‹‹በቃ እኔ የፈለኩት ይሄን ነው፤አየሽ ያልተጻፈ ነገር እየደበዘዘ ሄዶ ከእለታት አንድ ቀን መረሳቱ አይቀርም፡፡››

‹‹አይዞህ የሚረሳ ነገር አይኖርም፤መታተም አለበት ብዬ ስወስን ወደ አንተ ቢሮ እንደምመጣ ቃሌን እሠጥሀለሁ፡፡››

‹‹አመሠግናለሁ፤ቃልሽንም እንደምትጠብቂ አምናለሁ፡፡… ብቻ አሁን አንድ ነገር ላስቸግርሽ ነው...መጀመሪያ እሺ በይኝ፡፡››

‹‹ምን እንደምትጠይቀኝ ሳላውቅ እንዴት እሽ እላለሁ?»

‹‹በቃ እሽ በይኝ…ማድረግ የማትችይውን ነገር አልጠይቅሽም፡፡››

‹‹ለማድረግ እኮ ማድረግ መቻል ብቻ በቂ አይደለም...ፍላጎትም ያስፈልጋል፡፡››

‹‹ባክሽ ክርክሩን አቁመሽ እሺ በይኝ፡፡››

‹‹ውጪልኝ እንዳትለኝ እንጂ ለሌላው ችግር የለም፡፡››

ትክዝ ብሎ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡ እራቁት ገላዋ... ቅብጠቷ... የወሲብ ብቃቷ በዓይነ ህሊናው ተመላለሰበት፡፡

ከት ብላ ሳቀችና‹‹ ተነቅቶብሃል፡፡ በፍፁም እሺ አልልህም፡፡የእሱ ጉዳይ ተዘግቶ ፋይሉ ወደ መዝገብ ቤት ተመልሷል፡፡›› አለችው፡፡

‹‹ግምትሽ የተሳሳተ ነው፡፡ እርግጥ ፍላጎቱ የለኝም ብዬ ልዋሽሽ አልፈልግም… በጣም ተርቤሻለሁ፡፡ አሁን ቃል ግቢልኝ ያልኩሽ ግን ለእሱ አይደለም፡፡››

‹‹ለእሱ ካልሆነ ቃሌን ሠጥቼሀለሁ... ጠይቀኝ፡፡››

ጉሮሮውን በመጠኑ ካረጠበ በኋላ ‹‹ከዲያሪሽ ላይ የአንዱን ቀን ውሎሽን እንድታነቢልኝ እፈልጋለሁ፡፡››

<<መቼ>>

<<አሁን ነዋ>>

‹‹አይሆንም .. አይሆንም .. ሌላ ጊዜ፡፡››

‹‹ቃል ገብተሽልናል፡፡››

እንደማሰብ አለችና ‹‹እሺ... ምን ቸገረኝ.. ስለምንድነው መስማት የምትፈልገው? የዩኒቨርስቲ የህይወት ገጠመኜን፣ የቡና ቤት ህይወት ገጠመኜን .. የቱን?››

‹‹ደስ ያለሽን ...ግን…. ስለ ቡና ቤት ቢሆን እመርጣለሁ፡፡››

ወደ መኝታ ቤቷ በመሄድ ስለ ቡና ቤት የሕይወት ገጠመኟ ካሰፈረችባቸው ድያሪዎቿ መካከል አንዱን መዛ ወደ ሣሎን በመመለስ መቀመጫዋ ላይ ተመቻችታ ቁጭ አለች፡፡

‹‹እንግዲህ አዚህ ዲያሪ ላይ ከተፃፈው የአንዱን ቀን ውሎዬን ወይም አዳሬን አነብልሀለሁ፡፡ ግን መርጬ አይደለም፡፡ ዝም ብዬ እከፍተዋለሁ፤አነብልሃለሁ፡፡›ተስተካክላ ተቀመጠችና ዲያሪዋን ከፈተች ወደ መሃከል ገደማ ነው፡፡ ርዕሱን አነበበች ‹‹40 ፐርሰንት›› ይላል ....ይሄንንማ አላነብልህም በጣም ይሰቀጥጣል፡፡

‹‹እድሌ ነው አንብቢልኝ፡፡››

‹‹በናትህ ደባሪ እኮ ነው፡፡››

‹‹ምንም ቢሆን ምንም መስማት እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹እሺ ምን ቸገረኝ>> በማለት የገለጠችውን ዲያሪ በዝግታ ማንበብ ..…ሁሴን በጉጉትና በፀጥታ ማዳመጥ ቀጠለ

ሚያዚያ 20/2005

«40 ፐርሰንት››

ቀድሞ ገባ... ተከተልኩት፡፡ የቤርጎው ስፋት መታጠቢያ ክፍሉን ሳይጨምር አራት በሦስት ይሆናል፡፡ የከፈለኝ የጠየኩትን ያህል ብር ነው፡፡ ዝምተኛ፣ ጭምትና የከፋው ቢጤ ነው፡፡ እንዲህ አይነት ወንዶች አንድ የተለየ ነገር አይታጣባቸውም ብዬ ስለማስብ አብሬያቸው ማደር ደስ ይለኛል፡፡

የቤርጎውን በር ከቀረቀርኩ በኋላ ወደ ውስጥ ዘለቅኩ፡፡ ቀድሞኝ አልጋው ላይ ጋደም አለ ከነልብሱ፡፡ እኔም በእጄ ይዤ የነበረውን ኮንዶም ኮሞዲኖው ላይ ጣል አድርጌ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ሠረቅ አድርጌ ተመለከትኩት አይኑን ጣሪያ ላይ ሠክቶ ይቆዝማል፡፡ ነገር የገባው ፈላስፋ ይመስላል፡፡
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቢ


‹‹እሺ ሳባ ህይወት እንዴት ነው?››

‹‹አሪፍ ነው…ምንም አይል?››

‹‹ማለቴ የስራ ህይወትሽ እንዴት ነው..ደስተኛ ነሽ?››

‹‹አዎ በስራው ደስተኛ ነኝ….ግን ክፍያው በቂ አይደለም…ማለቴ  በቂ  ሊሆን ይችላል ለእኔ ግን እየበቃኝ አይደለም፡፡›› ስትል በምሬት መለሰችላት፡፡
‹ይገባኛል…አየሽ አንቺ የተማርሽ ቆንጆና ማራኪ ወጣት ብትሆኚም በዕድሜ ግን ገና ለጋ ወጣት ነሽ…ገና ብዙ ብዙ ዕድል ይጠብቅሻል.. በህይወት የተሰጠሸን እድል ትጠቀሚበታለሽ ወይስ ታባክኚዋለሽ….ዋናው ጥያቄ ይሄ ነው፡፡››

‹‹ማለት አልገባኝም፡፡››አለቻት..እውነትም አለመግባትም ብቻ ሳይሆን  ይባስ ብሎም ግራ ገብቷታል፡፡
ስለጀመረችላት ወሬ ይበልጥ ማብራሪያ ትሰጠኛለች ብላ ስትጠብቅ አሷ ‹‹እስኪ ተነሽ አንድ ቦታ ሄደን እንምጣ›› ብላት ቀድማት ከመቀመጫዋ ተነሳች...ሳባም ያለምንም ማቅማማት ተከትላት ተነሳችና ከኋላዋ ተከተለቻት፡፡
በፊት ለፊት በር ትወጣለች ብላ ስትጠብቅ ወደኋላ በር አመራች ..ረጅም ኮሪደር ሰንጥቀው ካቋረጡ በኋላ ወደውጭ ወጡ፡፡ በፅድና በተለያዩ አበቦችና አትክልቶች የተሞላ ውብ ግቢ ነው፡፡በረንዳውን ወርዳ ወደጓሮ ዘልቃ ገባች… ‹‹ይህቺ ሴትዬ ጓሮዋን ልታስጎበኘኝ ነው እንዴ?››እያለች  በማልጎምጎም  ተከተለቻት፡፡ግን ተሳስታ ነበር…፡፡እስከመጨረሻ ጓሮውን ሰንጥቀው ከጨረሱ በኋላ ሰማይ ጠቀስ በሆነው የብሎኬት አጥር መሀከል የሚያብረቀርቅ ወርቅ  ቅብ  አይነት  ቀለም የተቀባ የላሜራ ግዙፍ በር አለ..በራፉ ጋር አንድ ጥቁር  ሱፍ  የለበሰ  መልኩም ጥቁር የሆነ ወጠምሻ ሰው ቆሟል ፡፡
የኋላ ቤት የኋላ በራፍ በመኖሩ ተገርማ ሳትጨርስ ጭራሽ ጠባቂ ስታይ‹‹ይሄ ምን ጉድ ነው?››ስትል ነበር በውስጧ የጠየቀችው
‹‹….ሴትዬዋ ሀሽሽ አከፋፋይ ትሆን አንዴ?››መልስ ባታገኝም በውስጧ የጠየቀችው ጥያቄ ነበር፡፡ወጠምሻው ጠብ እርግፍ በማለት በትህትና እጅ ነሳና በራፉን ከፈተላቸው፡፡ተያይዘው በራፉን አልፈው ወጡ፡፡የወጡት ግን ወደ አስፓልት አይደለም ወይም ኮረኮንች መንገድ ላይ ወስዶ የሚጥልም አይደለም…ወደ ሌላ ግቢ እንጂ፡፡ ግቢው በግምት አንድ ሺ ካሬ ስፋት ያለው

ሲሆን የሎጅ አይነት አሰራርና አደረጃጀት የተከተለ ነው….ራቅ ራቅ ብለው አንደኛው ከአንደኛው በራፍና መግቢያ ተቃራኒ እንዲሆን ተደርጎ በቁጥር አስር በጎጆ ቅርፅ የተሰሩ ግድግዳቸው ባህላዊ ይዘት ኖሮት በተጠረበ ድንጋይ በጥንቃቄ የተሰሩ ቤቶች ዙሪያቸውን በተክሎች፤በአበባና፤በሀረጎች የተሸፈነና   የተከለለ ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡
ትብለጥም‹‹ይሄ አንደኛውና ዋነኛው የስራ ቦታችን ነው…ሌሎች ሁለት ቦታዎችም አሉን…ዋናው ግን ይሄ ነው፡፡››በማለት ወደ አንዱ እየመራች ወሰደቻት፡፡
የተዘጋውን በራፍ እጄታውን ጫን አለችና ገፋ አድርጋ ከፈተችው..ሶስት ክፍል አለው፡፡አንዱ ሻወር ቤት…ሁለተኛው ከሻወር  ቤቱ የተያያዘ  መልበሻ  ክፍል፤ሲሆን ሌላው ዋናውና ሰፋ ያለው ክፍል ነው፡፡ ሰፊውና ዋናው ክፍል ውስጥ አንድ ቁም ሳጥን ሁለት ደረቅ ወንበሮች፤ከአንድ አነስተኛ ጠረጴዛ ጋር አንድ መካከለኛ ቁመት ያለው ሰው በምቾት ማስተኛት የሚችል ረዘም ያለ በነጭ ቆዳ የተለበጠ ሶፋ ሲኖር ወለሉ መካከል ላይ ሰፊና ረጅም የማሳጅ  ጠረጴዛ አለ፡፡ዙሪያውን ቃኝታ ሳትጨርስ ደረቅ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ የነበረ አንድ የተወጣጠረ ጡንቻ ያለው ወጣት ከተቀመጠበት በፍጥነት ተነሳና ወደ እነሱ በመቅረብ  ‹‹እንኳን በሰላም መጣችሁ ›› ሲል መጀመሪያ ትብለጥን ከዛ ደግሞ ሳባን ጨበጣቸው…
ሳባ ሲጨብጣት የእጁ ልስላሴና ጥንካሬ ውስጧ ድረስ ተሰማት፡‹‹እንዴት በዚህ መጠን ለስላሳና ጠንካራ ሊሆን ቻለ..?››ስትል ተገረመችበት፡፡‹‹አይ  እንደዛማ ሊሆን አይችልም…እኔ ተሳስቼ ነው፡፡›› አለችና ትኩረቷን ለመሰብሰብ ሞከረች፡፡
‹‹ሶፈኒያስ ይባላል እሷዋ ደግሞ ሳባ ትባላለች…ዘመዴ ነች፡፡ሰሞኑን  ከተጨናነቀ ስራ ላይ ነበረች፤ከዛ አስነስቼ ነው ያስመጣኋት፤ትንሽ ዘና ማለት ይገባታል

…አንተን ደግሞ እተማመንብሀለሁ….ልከ ለእኔ እንደምታዳርገው ለእሷም እንደዛው፡፡›› የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈችለት፡፡
‹‹እረ ችግር የለውም…ግቢና ልብስሽን ቀይሪ…››ብሎ ፊቱን አዙሮ ወደ ጠረጴዛው ሄደና ለስራ የሚገለገልባቸውን ቅባቶችና የማሳጅ መገልገያ ዕቃዎች ማዘጋጀት ጀመረ፡፡ሳባ የምትለውና የምታደረግው ግራ ገብቷት በተገተረችበት ፈዛ ትብለጥን በትኩረት ትመለከታት ጀመረ፡፡
ገባትና ልትቀመጥ ወደሶፋው መራመድ የጀመረችውን እርምጃ ገትታ እጇን በመያዝ እየጎተተቻት ወደልብስ መቀየሪያው አነስተኛ ክፍል ይዛት ገባች.. የክፍሉ ሁለት የግድግዳው ክፍል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በመስታወት የተሸፈነ ነው፡፡በአንደኛው ግድግዳ ተደግፎ የቆመ ለክፍሉ እንዲስማማ ተደርጎ የተሰራ አነስተኛ ቁምሳጥን አለ…አንድ መቀመጫ መግቢያው ላይ አለ‹‹…በይ ልብስሽን አውልቂና ይሄንን ፎጣ አገልድመሽ ነይ…››
‹‹ልብሴን አውልቄ…? ማለት ለምን..?››

‹‹እንዴት ለምን ?ማሳጅ ተሰርተሸ አታውቂም?››

‹‹በፍፁም አላውቅም፡፡››

‹‹እንግዲያው እመኚኝ በጣም ትወጂዋለሽ፡፡›

‹‹እረ ይቅርብኝ..እኔ ወንድ ፊት እርቃኔን ቆሜ አላውቅም..››

‹‹እንዴ ምን ነካሽ የተማርሽና ዘመናዊ ሴት አይደለሽ እንዴ…? እንዳልሽ በወንድ ፊት ልብስሽን አውልቀሽ የማታውቂ ከዛም በላይ የወንድ እጅም ሰውነትሽ ላይ አርፎ የማያውቅ ሊሆን ይችላል…ግን ያ ማለት እስክትሞቺ   አንዲህ  ሆኖ ይቀጥላል ማለት እንዳልሆነ መቼስ በደንብ ታውቂያለሽ…አንድ ቀን በየተራ አድርገሽ የማታውቂያቸው ነገሮችን ቀስ በቀስ ማድረግሽ የማይቀርና የሚጠበቅ
ነው..አሁን በይ ልብስሽን አውልቂና ነይ…ደግሞ እኮ ብቻሽን አይደለሽም እኔ በክፍሉ ውስጥ ከፊት ለፊትሽ ቁጭ እላለሁ፡፡››
ምንም ማምለጫ መንገድ ልታገኝ አልቻለችም፡‹‹እሺ በቃ››

‹‹አዎ እንደዛ ነው የሚባለው..በይ አውልቂና ነይ .››ብላት ክፍሉን ጥላላት ወጥታ ሄደች…ሳባ የለበሰችውን ቀሚስ አወለቀችና ቀኑን ሙሉ ስትለፋበት የዋለችውን አዲስ የተሰራ ጸጉሯን አንድላይ ጠቅላላ በማያያዝ ፎጣውን አገልድማ ልክ ለዘመናት ሲያልመውና ሲመኘው ወደከረመው መድረክ   አድል ቀንቶት ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚወጣ አማተር  አርቲስት በፍራቻና   በሚንቀጠቀጡ እግሮቿ ወደ ውስጥ ገባች…ሁለቱም ቀና ብለው አዯት እና እርስ በርስ ተያዩ
…ፈገግ አለች ትብለጥ

‹‹ምነው?ምን አጠፋሁ?››

‹‹ምንም…ግን በማሳጅ ምንም አይነት ልብስ አይፈቀድም…››

‹‹እንዴ ፓንትም?››

‹‹እሺ ለዛሬ ፓንቱን ይሁን ተይው…ጡት ማስያዣውን ግን አውልቂው…››

‹‹ሴትዬዋ ጉድ ልትሰራኝ ነው እንዴ? ያን  ሁሉ  እንክብካቤና  ጠብ  እርግፍማ ለጤና አይደለም›› እያለች ተመልሳ  ወደክፍሉ  ገባችና  ጡት  ማስያዣዋን አወለቀችና ተመለሰች…ወደ ጠረጴዛው ቀረበች…
‹‹ዘና በይና ጠረጴዛው ላይ በደረትሽ ተኚ ››አላት…

ከፍራቻዋ ጋር እየታገለች እንዳላት አደረገች..ቅባቱን በእጆቹ አፈሰና  ከትከሻዋ አካባቢ እጆቹን አሳረፈ፡፡ ሰውነቷ ሽምቅቅ  አለ…ቀስ  እያለ  መገጣጠሚያዋን እየነካካ እያፍታታት፤ወደታች ወደ ጀርባዋ ወረደ…አንዳንዴ ላላና ለስለስ ብሎ
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹ይሄ መንገድ ግን ወደ መጣንበት አቅጣጫ የሚወስድ አይደል እንዴ?››በጥርጣሬ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ አይደለም…..ትንሽ ከተጓዝን በኃላ እንታጠፋለን፡፡››ሲል ድጋሜ ዋሻት፡፡

ከዛ በኃላ ለ10 ደቂቃ ያህል ጫካውን ቁጥቆጦ እየገፉና እሾክና እንቅፋቶችን ከፊታቸው እያስወገድ ወደፊት ከመጓዝ ውጭ በሶስቱም መካከል ምንም ንግግር አልነበረም፡፡
ኑሀሚ የህይወቷ የመጨረሻ ጫፍ ላይ እንደደረሰች ተስምቷታል፡፡ከቡድኑ ነጥለው ወደጫካው እየነዷት ያለው ለሰላም እንዳልሆነ ወዲያው ነው የገባት፡፡ በተለይ የካርሎስ መርበትበትና በፊቱ ላይ እየተመለከተችው ያለው ሀዘን በጥርጣሬዋ እርግጠኛ እንደትሆን አድርጓታል፡፡ በዛ ላይ ከኃላ ሆኗ የሚከተላቸው ፊቱ የማፈታው ታጣቂ በጀርባው ባነገተው ቦርሳ አካፋም መቆፈሪያም ሆኖ የሚያገለግል ወታደሮች ምሽግ ለመስራት የሚጠቀሙበትን መሳሪያ ይዞ በማየቷ ሌላ እርግጠኛ እንድትሆን ያደረጋት ምልክት ነው፡፡
አካባቢን ማጥናት..ማንኛውንም እንቅስቃሴ በንቃት መከታተል..ከዛ የይሆናል ትንበያዎችን አስቀምጦ ከቅርቃሩ ለመውጣት የሚያስችሉ አማራጮችን በፍጥነት ማስላት….በስለላ ህይወቷ የቀሰመችው ትምህርት ነው፡፡
እና ዝም ብላ መሞት እንደሌለባት እራሷን እያሳመነች ነው፡፡በህይወቷ እንዲህ መሰል በህይወትና በሞት ቅርቃር መካከል የመውደቅን አጋጣሚ ብዙ ጊዜ ገጥሞት ያውቃል፡፡ በአምስት ሰዎች ተከባ ልትገደል ብላ ግማሹን ገንድሳ ግማሹን ገድላ ነፃ የወጣችበትና ህይወቷን ያተረፈችበት አጋጣሚ ነበረ፡፡ከእዛ አንጻር ሲታይ ይሄ ቀላል ይመስላል..ምክንያቱም ከሁለት ታጣቂዎች ጋር ነው የምትፋለመው፡፡ ካላት ወታደራዊ እውቀትና ልምድ አንፃር አነሱን ገድላ ወይ ፌንት አስበልታ የማምለጥ እድሏ ከ50 ፐርሰንት በላይ ነው ፡፡..ችግሩ ካመለጠች በኃላ ነው፡፡ፊቷ ያፈጠጠው ምኑንም የማታውቀው በየት ገብታ በየት መውጣት እንዳለባት ምንም እውቀት የሌላት የአማዞን ጫካ ነው፡፡ጫካ ውስጥ ያሉት አስፈሪና በስም እንኳን ለይታ የማታውቃቸው አውሬዎችና አንድ ጠብታ መርዛቸው እንኳን ሰውነት ላይ ሲያርፍ በሰከንድ ውስጥ የሚያደርቅ ተሳቢ እንስሳትና በራሪ ነፍሳት ጋር ነው፡፡ቢሆን በሰው ተቦጫጭቆ ከመበላት በአውሬ ጋር ለመፋለም ቁርጠኛ መሆን ይሻላል
፡፡በዚህ ቅፅበት አንድ ታሪክ ትዝ አላትና ለካርሎስ ልትተርክለት ፈለገች፡፡

‹‹አንድ ጣፍጭ ታርክ ልንገርህ?››

እንደ እሱ ግንዛቤ ሰዓቱ ታሪክ መንገሪያም ሆና ማዳመጪያ እንዳልሆነ ቢያምንም ለእሷ ግን ምን አልባት የመጨረሻ ቃሏ ሊሆንላት ይችላል ብሎ ስላሰበ እንድትነግረው ተስማማ፡፡
‹‹ጨቋኝ ገዢ ወይም የሰው ልጅ  ከገዳይ ነብር የበለጠ አስፈሪ እንደሆነ የሚያስረዳ ታሪክ ነው፡፡
‹‹ገባኝ ንገሪኝ…››

ከአንድ የድሮ መፅሀፍ ላይ ያነበብኩት ታሪክ ነው፡፡በአንድ ወቅት በቻይና ግዛት ውስጥ በምትገኘው በታይ ተራራ ስር በሀዘን ተቆራምዳ እንባዋን እያዘራች የምትኖር ሴት ነበረች፡፡የዚህችን ሴት ታሪክ ኮንፌሽዬስ ሰማና አስጠራት፡፡ከዛም"አንቺ ሴት ምን ሆነሽ ነው እንዲህ ሀዘን የበላሽ?"ሲል ጠየቃት።ሴቲቱም ‹‹በተራራው ላይ የሚኖረው ነብር ባሌን ፣የባሌን አባት እና ብቸኛ ልጄን በየተራ እየቀረጣጠፈ በላብኝ-በዛ ምክንያት ነው ሀዘኔ ጥልቅ የሆነው›› ብላ መለሰችለት።
እሱም መልሶ "ታዲያ መላ ቤተሠቦችሽን የበላው ነብር አሁንም በተራራው ላይ መኖን እያወቅሽ .እንዴት ከአካባቢው ሳትሸሺ?››ሲል በመገረም ጠየቃት።
ሴቲቱም‹‹ቦታውን ለቅቄ ያልተሠደድኩት ጨካኝ ገዢ የሌለበት ብቸኛ  ስፍራ ስለሆነ ነው።"ስትል መለሠችለት
ኮንፌሽዬስም ወደ ደቀመዛሙርቱ ዞሮ" አያችሁ ጨቋኝ ገዢ ከገዳይ ነብር የበለጠ አስፈሪ እንደሆነ ከዚህች ሚስኪን ሴት ታሪክ ተማሩ፡፡›› አላቸው።
እኔም አሁን እዚህ አማዞን ደን ውስጥ ካሉት አውሬዎች በላይ ጨካኝ የሆኑ የሰው ልጆች ናቸው እያሰፈሩኝ ያሉት››ብላ ታሪኩን ደመደመች፡፡
‹‹አልተሳሳትሽም….የሰው ልጅ መጨከን ከጀመረ ወሰኑ አይደረስበትም…››

‹‹እኔ ምልህ ..አሁን ልትገድሉኝ ነው አይደል?››

ጥያቄዋ አስደነገጠው…ምን ብሎ እንደሚመልስላት ግራ ስለገባው…ዝም አለ…‹‹አትጨነቅ..ግን ያልገባኝ እንዲህ ልትገድሉኝ ይሄን ሁሉ ቀን እኔንም ማንከራተት እናንተም ከእኔ ጋር መንከራተት ለምን አስፈለገ?››
‹‹ትዕዛዙ የደረሰን አሁን ነው…››

‹‹ትዕዛዙን የሚሰጠው ማን ነው››

‹‹ሀለቃችን ነው…ካለበት ቦታ በሳተላይት መገናኛ ነው ከደቂቃዎች በፊት ትገደል ያለው፡፡››

‹‹ይገርማል…ቆይ ግን ከእኔ ጋር ያገኛችሁትን ሰውዬ ገድላችሁታል አይደል?››

ፈገግ አለ፡፡

የፊቱን ፈገግታ በቆረጣ እይታ አየችውና ተበሳጨችበት…‹‹ምነው? የሰው መገደል ያስቃል እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም … እንደውም በተቃራኒው ልቤን ነው የሚሰባብረው፡፡››

‹‹አይ ስትስቅ አየሁህ ብዬ ነው፡፡››

‹‹ጥያቄሽ ነው ያሳቀኝ …አንቺ እንድትገደይ ትዕዛዙን ያስተላለፈው ሀለቃችን አሁን አንቺ የምትጨነቂለት ዳግላስ መሆኑን ሳስብ ነው ያሳቀኝ..አየሽ አለም በእንደዚህ ይነት ገራሚ ምፀቶች የተሞላች ነች፡፡››
እርምጃውን ገታችና ባለችበት ቆመች..ከኃላ እየተከተላቸው ታጣቂ አይኑን አጉረጠረጠ…የጓደኛውም ሆነ የተገዳዮ ነገረ ስራ ምንም አላማረውም…ጣልቃ ላለመግባት ነው እንጂ ወሬያቸውም አልተመቸውም.. ምክንያቱም እሱ ስፓኒሽኛ ተናጋሪ ሲሆን እንሱ እያወሩ ያሉት በእንግሊዘኛ ነው..እሱ ደግ እንግሊዘኛ ጆሮውን ቢቆርጡጥ አይሰማም፡፡
‹‹ማለት ከእኔ ጋር ያገታችሁት በሌላ ጀልባ ወደሌላ ስፍራ የወሰዳችሁት ዳግላስ የእናንተ ሀለቃ ነው?››ማመን ስላልቻለች ደግማ ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እሱ የእኛ ብቻ ሳይሆን በሺ ሚቆጠሩ ሌሎች የታጣቂ ቡድኖች መሪ የጫካው ንጉስ እየተባለ   የሚጠራ   ከፍተኛ   ቢሊዬን   ዶላሮች   የሚያንቀሳቅስ   ከፔሩ፤ ኮሎምበያ፤ ፓናማ፤ ነካረጎ፤ ጉታማላ፤  ሚክሲኮ አልፎ አሜሪካ ድረስ እሱ የሚቆጣጠረው የንግድ መስመር ያለው በሶስት በአራት ሀገራት የደህንነት ሰዎች ሚፈለግ አለማ አቀፉ የኢንተርፖል የተፈላጊዎች ስም ዝርዝር ውስጥ የመጀመሪያው ገፅ ላይ የሰፈረ ተአምረኛ ሰው ነው፡፡››የሚላትና ማመን ነው እያቃታት፡፡‹‹እና እሱ እንደእዛ አይነት ሰው ከሆነ ለምን ከእኔ እኩል አፈናችሁት?፡፡››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ሰውዬው መድሀኒቱን በጊዜ ካልወሰደ ከፍተኛ የመርሳት ችግር አለበት..ማለት እራሱንና ማንነቱን ሙሉ በሙሉ እስኪዘነጋ ድረስ ይደርሳል፡፡ከንቺ ጋር ሊማ አየር ማረፊያ ተገናኝታችሁ ኢኩቶስ እስክታርፉ ድረስ ከዛም ሆቴል ይዛችሁ ስታድሩ ሁሉ ያገጠማችሁ ያ ነው፡፡በወቅቱ ችግሩ እንደተፈጠረ ስናውቅ በግል ቻርተር አውሮፕላን እናንተ ወዳላችሁበት መጣን፡፡ ቀጥታ ሄደን ብናናግረው..አላውቃችሁም ሊለን ይችላል፡፡ ክርክር ብንገጥም ጭቅጭቅ ቢነሳ ደግሞ ትኩረት እንስባለን…እንዳልኩሽ በአለም አቀፍ ደረጀ የሚፈለግ ሰው ነው…ስለዚህ ሁኔታውን አመቻችተን ማፈን ነበረብን፡፡ለዛ ነው እንደዛ ያደረግነው፡፡››
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧

እለቱ እሁድ ነው፡፡ከፊራኦል ጋር ለመውጣት ስለተነጋገሩ እየተዘጋጀች ነው፡፡ለሊሴ እየረዳቻት ነው፡፡
ሰው ከለገመ ከሻማ በላይ በቀላሉ ቀልጦ የሚጠፋ ከጠነከረ ደግሞ ከአልማዝም በላይ ማይቆረጥና ማይሸረፋ ተአምራዊ ፍጡር መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡በፀሎትም የማያልፍ የመሰላት አሰቃይ ህመም በጥቂት ቀናት ውስጥ ጥሏት ሄዶ ንፅህና ጤነኛ ልጅ ሆናለች፡፡የእግሯን ስብራት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ድኗል…የፊቷ ቁስል ግን ምንም እንኳን ቢድንም ጣባሳውና ቁስለቱ አሁንም በግልጽ ፊቷ ላይ ይታያል… በዚህ ምክንያት አሳባ ከፊል ፊቷን ሁሌ በሻርፕ እንደሸፈነችው ነው፡፡ዋና ምክንያቷ ግን ማንነቷ በቀላሉ እንዳይለይ በማሰብ ነው፡፡አሁንም ተመሳሳይ አለባበስ አድርጋ በዛ ላይ ጥቁር መነፅር አይኗ ላይ ሰክታ ዝግጁ ሆነች፡፡

‹‹ግን እህቴ ለምንድነው እኔን የማታስከትሉት?››ለሊሴ ተነጫነጨች፡፡

‹‹አይ …መጀመሪያ ከወንድሜ ጋር የምንሄድበት ቦታ አለ…ባይሆን ከዛ ቶሎ ከጨረስን እንደውልልሽና ትቀላቀይናለሽ››

‹‹ይሁንላች ግን ታበሳጭቼባችኋለሁ››

በታክሲ ከሰፈር ሁለት ፌርማታ ያህል ርቀው ከሄዱ በኃላ ‹‹ደርሰናል እንውረድ›› አላት፡፡ያን ያህል ቅርብ ይሆናል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡እንደወረዱ ቀጥታ ፊት ለፊት የሚገኝ በፅድና በባህርዛፍ አፅድ የደመቀ ሰፊ መናፈሻ ውስጥ ነው ይዞት የገባው…ቀጥታ ከሰው ነጠል ያለ ቦታ ይዞት ሄደና ቁጭ እንድትል መቀመጫ አመቻችቶላት ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ‹‹እሺ ምን ትጠቀሚያለሽ?››

‹‹ቆይ እስኪ… ምን አስቸኮለህ…መጀመሪያ ትምጣ››

‹‹ማን?››

‹‹ምን ….ማንን ልናገኝ ነው የመጣነው…?ፍቅረኛህ ነቻ…በል ደውልላት፡፡››

‹‹ስልክ የላትም››

‹‹ታዲያ እንዴት ነው የምታገኘን››
‹‹የልቤን ምት አዳምጣ ትመጣለች››

‹‹ጥሩ ትቀልዳለህ….ይሄ የተለመደ መገናኛ ቦታችሁ ነው ማለት ነው…ገባኝ›› አስተናጋጁ መጣችና‹‹ምን ልታዘዝ ?››ብላ ጠየቀች፡፡

በፀሎት ቀደም ብላ‹‹ሰው እየጠበቅን ነው….››ብላ ለአስተናጋጆ መለሰችላት

‹‹አይ አሷን አንጠብቅም..ቆንጆ ፒዛ አሰሪልን…ፒዛው እስኪደርስ እሷም ትደርሳለች››

አስተናጋጆ ትዕዛዙን ተቀብላ ሄደች፡፡

ፊራኦል ወደእሷ አትኩሮ እያያት…..‹‹እስኪ ሻርፑን አንሺው››በማለት ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት

‹‹እንዴ ለምን?››

‹‹ሙሉ ፊትሽን ለማየት ፈልጌ››

‹‹ኖ ዌይ…..›

‹‹ምን ችግር አለው?››

‹‹እኔ  እራሴ  ሙሉ  በሙሉ  ፊቴ  እንደዳነ  እና  እንደማያስጠላ  እርግጠኛ  ስሆን እገልጠዋለው፡፡››

‹አንቺ እንዴት ልታስጠይ ትችያለሽ…ውብ እኮ ነሽ››

‹‹ሙሉ ፊቴን ሳታይ ውብ መሆኔን በምን አወቅክ…?››ኮስተር ብላ በመገረም ጠየቀችው፡፡

‹‹እኔ እንጃ ውብ እንደሆንሽ ግን እርግጠኛ ነኝ፡፡››

መልስ ልትሰጠው አፏን ስትከፍት አስተናጋጇ የታዘዘውን ፒዛ ይዛ ፊታቸው ስታስቀምጥ አፏን ያለምንም ንግግር ከደነች፡፡

‹‹‹ለእኔ እስፕራይት አምጪልኝ…..ላንቺስ ?›

‹‹እንዴ ልጅቷ ሳትመጣ….?››
‹‹ባክሽ የሆነ ነገር እዘዢ እሷ ስትመጣ የራሷን ነገር ታዛለች››

ግራ እየገባት አዘዘች …ፒዛውን ቆርሶ መብላት ሲጀምር ፣ በገረሜታ ተከተለችው… በልተው ጨርሰው እንኳን ልጅቷ አልመጣችም››

‹‹እንደዛ  ቅኔ  ምትቀኝላት  ልጅ  እስከአሁን  ካልመጣች  ከአሁን  ወዲያም  የምትመጣ አይመስለኝም፡፡››

‹‹መጣችእኮ››

‹‹የታለች?››

‹‹ይህቹት ፊት ለፊቴ ቁጭ ብላ እያወራቺኝ ነው፡፡››

‹‹እየቀለድክብኝ ነው እንዴ?››

‹‹እሺ አትበሳጪ..እኔ ምንም አይነት ፍቅረኛ የለኝም….አንቺን ወጣ አድርጌ ማዝናናት ስለፈለኩ ነው እንደዛ ያልኩሽ››

‹‹አንተ ውሸታም……..ቆይ ምንም ፍቅረኛ ሳይኖርህ ነው እንደዛ ፈዘህ በውድቅት ለሊት ቅኔ ስትዘርፍ የነበረው››

‹‹በተጨባጭ ፍቅረኛ የለኝም አልኩሽ እንጂ በምናቤ ስዬ የማስባት ሴት የለችም አላልኩሽም…..እንደዛ አወራ የነበረው በልቤ ውስጥ ተንሰራፍታ የተቀመጠችውን ልክ እንደአንቺ ውብ የሆነችውን ልጅ እያሰብኩ ነበር››

‹‹ምን አይነት አዝግ ልጅ ነህ….?እኔ ደግሞ እንዴት አይነት ቆንጆ ልጅ ትሆን እያልኩ ለሊቱን ሙሉ ሳስብና ስጓጓ ማደሬ››

‹‹ምን ያጓጓሻል…የፈለገ ውብ ብትሆን ካንቺ አትበልጥ…አንቺ እኮ ሁለመናሽ ውብ ነው…ማለት ስብዕናሽ ፖስቸርሽ..እርግጠኛ ነኝ መልክሽም ውብ ነው..ፍቅረኛዬ ልክ አንቺን ካልመሰለች ልቤን ማሸነፍ አትችልም››ፊራኦል ቀጥታ መንገር ፈርቶ ነው እንጂ ከበፀሎት ፍቅር ከያዘው ሰነባብቷል…ስሩ ሆና እራሱ ትናፍቀው ከጀመረች ቆይታለች..ለዛ ነው ሙሉ ፊቷን ማየት በጣም የናፈቀው…ቆንጆና ውብ ፊት ነው በምናቡ የሳለው…
‹‹ጥሩ ..ግን ስለውበትና ቁንጅና እኮ በእህትና በወንድም መካከል የሚወራ ኮንሰፕት አይደለም…..ባምርም ባስጠላም እንደእህትህ ነኝ…ለውጥ አያመጣም፡፡››

‹‹እንደእህት እና እህት ግን ይለያያል››

ለዚህ ንግግሩ ምን ብላ መልስ ልትሰጠው እንደምትችል ሊመጣላት አልቻለም…‹‹.እኔ የእህትህን ልብ በውስጤ የተሸከምኩ ሴት መሆኔን ብታውቅ ይሄን ሁሉ ርቀት ለመጓዝ አይዳዳህም ነበር››ስትል በውስጧ አብሰለሰለች

//////

በማግስቱ-----
እቤት ውስጥ ማንም የለም..ሌንሳ ብቻ ከበፀሎት ጎን ቁጭ ብላ እያወራቻት ነው፡፡
እህቴ ስራ በማግኘቴ በጣም ደስተኛ ሆኜያለው….ይገርምሻል ፀሀፊ ሆናለው ብዬ አንድም ቀን ኣስቤ አላውቅም ነበር…››

‹‹ላንቺ እኔ በጣም ደስ ብሎኛል… ስራውን ግን እንዴት ነው..እየለመድሽው ነው? ››

‹‹አሪፍ ነው ..ተመችቶኛል፡፡››
‹‹የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ነው ያልሽው?››

‹‹አዎ እህቴ …ብታይ ሰውዬው ማለቴ አለቃዬ በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡››

‹‹ለምንድነው የሚያሰዝነው? እሱም ፍቅር ይዞታል እንዴ?፡፡››

‹‹አይ እሱን አላውቅም … ያሳዝናል ያልኩሽ…ምንም ደንበኛ የለውም….ዝም ብለን እኔና እሱ ቢሮ ውስጥ ተፋጠን ነው የምንውለው…››ለምን ያሳዝናል እንዳለች ታስረዳት ጀመር፡፡

‹‹ምነው በስራው ጎበዝ አይደለም እንዴ?››

‹‹አረ በቅርብ ነው ከውጭ የመጣው..በሞያው ኤክስፐርት ነው…እንደነገረኝ ከሆነ አሜሪካ እያለ በሞያው ከሶስት አመት በላይ ሰርቶ በጣም ብዙ ሰዎችን ረዳቷል …እዚህ መጥቶ የራሱን ድርጅት ቢከፍትም እንዳሰበው አልሆነለትም….እንደምታውቂው የእኛ ሰው ድብቅ ነው …ባለትዳሮችም ቢሆኑ እዛው ቤታቸው ውስጥ ሲቋሰሉ ይኖራታል እንጂ ገበናቸውን ወደአደባባይ ማውጣት አያስብትም ..ባስ ቢልባቸው እንኳን እዛው የሰፈር ሽማጊሌ ጠርተው በምስክር ፊት ይጨቃጨቃሉ እንጂ ወደባለሞያ አይሄዱም፡፡ለዚህ ጉዳይ ባለሞያም እንዳለው የሚያውቅ የማህበረሰብ ክፍል አንድ ፐርሰንት የሚሞላ አይመስለኝም፡
‹‹ታዲያ እኮ የሰፈር ሽምግልናው ቀላል ነገር አይምሰለሽ…ሁለቱም ለእኛ ጥሩ ያስባል እና ያስማማናል የሚሉትን ሰው በማሀከላቸው አስቀምጠው ችግራቸውን በግልፅ በመነጋገር
ለመፍታት መሞከር ትልቅ ዋጋ ያለው ማህበራዊ እሴታችን ነው፡፡በዚህም መንገድ በጣም በርካታ ሺ ትዳሮች በየአመቱ ስንጥቃቸው ይደፈናል ስብራታቸው ይጠገናል፡፡››
#የጣት_ቁስል


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ

የማን ይሁን ?

የባሰ! እሾክና መርፌ ተነቅሎ የማይጣል፤ በቅርብ ሳይገፋ ያልተደረሰበት ፤ ከላይኛው የወረደ ዱብዳ ፤ የፈጣሪ የቁጣ ስጦታ፡፡ ለማን ታድርገው? ለማን ትስጠው? ለማንስ አቤት ትበል? ተቆርጦ የማይጣል የጣት ቁስል ሆነባት፡፡

ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረ፡፡ እንደ ተዳፈነ እሳት ውስጧን አቃጠለው፡፡ እንደ ሰኔ ደመና አረምሞ ገፍቷል፡፡ በአንድ ቀን ስህተት የእግዚአብሔር ስራ እንኳን ባይባልም በመቅሰፍቱ በዲያቢሎስ ቅንብር ሆዷ ውፍረትን መከታ እና ከለላ ተጠቅሞ ሳይታወቃት እየገፋ መጥቷል፡፡

እድላዊት ከወንድሟ ከተመስገን ፀንሳለች፡፡ በአንድ እንዴት ላረግዝ እችላለሁ?፡፡ ስታዝን ስትጨነቅ ዘጠኝ ወር ተቆጥሮ ቦርጩ ወደ ልጅ ተቀየረ፡፡ ወንድ ልጅ ከነ ቃጭሉ ተገላገለች፡፡ ግን ከፊቷ አሁንም የማይገፋ ከዳቢሎስ የተገነባ የጨለማ ተራራ ተጋርዶባታል፡፡

ምንጃር ሸንኮራ አውራጃ ውስጥ ነው፡፡ ጉራንባ ማርያም አካባቢ ያለ ማህበረሰብ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡ በእምነታቸው አክራሪና ከእምነት ውጭ ለሚከሰቱ ማንኛውም የክርስትና ጥፋት የፈፀመ ከማህበረሰቡ ይገለላል፡፡ እንደ እድር ፣ ባልትና እና ማህበር የመሳሰሉትን መካፈል አይችልም፡፡ በማህበረሱቡ የተጠላ ፤የማይወደድ ፣ ከሰው እንዳልተፈጠረ ከሰው ውጭ ተደርጎ ይቆጠራል።

እድላዊት እያወቀች ሳይሆን ሳታውቅ ከወንድሟ ከተመስገን መውለዷን ከያሬድ ውጭ ማንም አያውቅም፡፡

የወለደችውን ልጅ ክርስትና የሚነሳው የወላጅ አባት ስም ካልታወቀ መነሳት ፤ መጠመቅ የተወገዘና የተከለከለ ነው፡፡ የእድላዊት ልጅ ባለማወቅ አባት ታዲያ ማን ይሁን ? የማንስ ተብሎ ክርስትና ይጠመቅ ? አክ ተብሎ የተተፋ ምራቅ ተመልሶ አይዋጥ፡፡ የተመስገን ብትለው ለእሷ አንዴ ሞት ቢሆንም ለዘመዶቿና ለቤተሰቦቿ አስሬ ሞት ብቻ
ሳይሆን ከሰው እንዳልተፈጠሩና ወግ አጥባቂ የክርስትና አገልጋይ እንዳልሆኑ ከሰው ውጭ ተደርገው እንደሚገለሉ የሚታወቅ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡

ታዲያ እድላዊት ይህ ሁሉ የታዘለባትን የጭንቀት እሳት ማማከር ያለባት ለወንድሟ ለተመስገን እንጅ ለማንም ማማከር እንደ ማይቻል ግልፅ ነው፡፡ ግን አሁንም ሌሊቱ ጨልሞባታል፡፡

"ምን እናድርግ ? የልጁ የክርስትና ቀን እየደረሰ ነው፡፡ እኔ ጨንቆኛል፡፡ የማደርገው ጠፍቶኛል፡፡ ከእንግዴህ ያለኝ አማራጭ መርዝ ጠጥቸ ወይም ታንቄ መሞት ነው፡፡ የወንድሜ ነው ብየ ክርስትና አላስነሳም፡፡ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡

ተመስገን የእህቱ ጭንቀት በሱም ላይ ካደረበት እና ከሰነበተበት ቆይቷል፡፡ ጥሎ እንዳይጠፋ እድላዊትን ተመልሶ ዳግመኛ የማያገኛት መሰለው፡፡

እድላዊት እያለቀሰች መልስ እንኳን ሳይሰጣት ከያሬድ ጋር ደርሸ መጣሁ ብሏት ተነስቶ ወደ ያሬድ ቤት ሄደ፡፡

ተመስገን እንደደረሰ ከያሬድ ጋር የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ ያሬድ ወደ እርሻ ሊሄድ ሞፈርና ቀንበር እያዘጋጀ ነው፡፡

"ወደ እርሻ ልትሄድ ነው እንዴ ሞፈርና ቀንበር የምታሰናዳው?" አለ ፤ ተመስገን፡፡

"አዎ፤ እንዴው ትንሽ የፋልማ መሬት ከሰም ነበረኝ፡፡ ቧጠጥ አድርጌያት ልምጣ ብዬ ነበር አነሳሴ፡፡ ስተረካከም እዚሁ እረፈደ ብሎ ወደ ቤት ግባ እንጅ አለው፡፡

"ኧረ አልገባም፡፡ አንተ ጋር ነበር የመጣሁት"፡፡

"ምነው በደህና ነው"? አለ ፤ ያሬድ፡፡

"ምን ደህንነት አለ ፤ ገና ስፈጠር የአርባ ቀን እድሌ በእሳት ተሞልቶ የእሳት እረመጡ ወደ ጭስነት ተቀይሮ የመውጭያ በር አጥቶ በቁሜ እያቃጠለኝ፡፡

"ምነው እድላዊት ሰላም አይደለችም እንዴ?፡፡

"አይ! ተወኝ ፤ አሁን የእድላዊት ነገር አስጨንቆኛል፡፡ የልጁ ክርስትና እየደረሰ ነው፡፡ የአባቱ ስም ካልታወቀ ክርስትና እንደ ማይጠመቅ አንተም ታውቃለህ፡፡

የማደርገው ሁሉ ግራ ገብቶኛል፡፡ ወንድሜ እባክህ ከዚህ ጨለማ አውጣኝ፡፡ ያላንተ ማንም የማዋየውና የማማክረው የለኝም አለው፡፡በሃዘን ተሞልቶ ፡፡

"በምን ልርዳህ የማደርገው ጠፍቶኝ እኮ ነው፡፡ እስከ አሁንም ዝም ያልኩህ እንጅ እኔ እንኳን ወደ አዲስ አበባ ይዘናት እንድንሄድ አስቤ ነበር፡፡ ግን ክርስትና ሳታስነሳ ከቤት መውጣት አይቻልም ብየ ነው፡፡ አሁን በምን ላግዛችሁ ? ንገረኝና በተቻለኝ አቅም ልሞክር አለ፡፡

በፊቱ ላይ ወርዶ ቡሃቃ ያስመሰለውን እንባ በለበሰው ፎጣ እየጠራረገ እኔማ ለመጥፋትም አስቤ ነበር፡፡ ግን እድላዊት ጥሎ የሚሄድ አንጄት አጣሁ፡፡ አሁን አንተን የማስቸግርህ ልጁ ክርስትና እስከሚነሳ ድረስ የአባቱን ስም በአንተ እናድርግና ክርስትና ከተጠመቀ በኋላ ፤ የተፈጠረውንና የተደረገውን ባለመተዋወቅ እንደ ሆነ ለቤተሰብ እንነግራለን አለ፤ ተመስገን ፡፡ ደፍሮ በመናገሩ አይኑን ላለማየት አቀርቅሮ መሬት መሬት እያየ፡፡

የልጁ አባት ሆኘ ክርስትና ቢጠመቅ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን የአካባቢያችንን ባህል እንደምታውቀው በሚስቱ ላይ ዲቃላ ወልዷል ተብየ እኔ ከማህበረሰብ እንደምገለል፡፡ ደግሞም ባለቤቴ ይህንን ስሰማ በእኔ ላይ ዲቃላህን ታንጠባጥባለህ ብላ ባዶቤት ዘግታብኝ ትሄዳለች አለ ፤ ያሬድ፡፡

"ያልከው ሁሉም ይገባኛል፡፡ ግን ከወንድሟ ወለደች ቢባል ምን ያህል እንደሚከብድ መገመት አያቅትህም፡፡ ደግሞ አባታችን በዚህ ቦታ ወግ አጥባቂ እንደ ሆነ ታውቃለህ፡፡

እባክህ! ያሬድ ስለፈጠረህ አምላክ! ተለመነኝ ሳላውቅ እንደ ሆነ እሳት ውስጥ የገባሁት አንተም ታውቃለህ፡፡ ሚስጥሩን ለባለቤትህ እንነግራታለን፡፡ መጀመሪያ አንተ ብቻ እሽ በለኝ፡፡ እያለቀሰ ተማፀነው፡፡

ያሬድ የሚለው ሁሉ ጨነቀው፡፡ የእድላዊትና የተመስገን ስቃና መከራ የሱም ሆነ፡፡ ክርስትናው እስከሚያልፍ የልጁ አባት ለመሆን ብቻውን መወሰን አልቻለም፡፡

"ለማንኛውም አበበችን አብረን ሚስጥሩን እናካፍላትና እሷ እሽ ካለች የእኔ አያስቸግርም፡፡ አይቻልም ካለች ግን ምንም ላደርግ አልችልም" አለው

"እሽ አንተ እንዳልክ" ብሎት ወደ ቤት ገቡ፡፡

"ደህና አደርሽ አበበች" ? አለ ፤ ተመስገን፡፡

"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርክ ተመስገን" ? አለች ፤ አበበች፡፡

ጉንጮቹ አብጠው ገና በጥዋቱ አይኖቹ ቀልተዋል፡፡

ምነው ደህና አይደል ይሆን ? ያለቀሰ ይመስላል፡፡ የሞተ ሰው ይኖር ይሆን ? ያሬድም ደስተኛ አይመስልም፡፡ ዛሬ ምን ተፈጥሮ ይሆን ? አበበች ከውስጧ ሳታወጣና ሳታሰማ የተናገረችው ነበር፡፡

ምን ብሎ እንደሚነግራት ግራ ተጋብቷል፡፡ የቤቱን ጣራ ጣራ እየተመለከተ እንባው በጉንጩ ላይ ይወርዳሉ፡፡ አንገቱን ዞር አድርጎ ለመጥረግ ሞክረ፡፡

አበበች ግን ገና ሲገባ አንስታ እየተመለከተችው ነበር፡፡

"ምነው ደህና አይደለህም እንዴ? የምታለቅሰው" አለች ፤ ለተመስገን፡፡ የተፈጠረውን ለመስማት እየተጨናነቀች፡፡
ተመስገን ከተቀመጠበት ብርጩማ ላይ ተነስቶ ምንም በማታውቀው እና ምንም ባልሰማችው አበበች እግር ላይ ተደፋ፡፡ እባክሽን ከጉድ አውጭኝ ፤ በምትወጅው ልጅሽ ፤ በምትኩ ስም እለምንሻለሁ እያለ ያለቅስ ጀመር፡፡

አበበች ተመስገን ስለምን እንደሆነ የሚያወራው ግራ ተጋብታለች፡፡ ሲለምናትና ሲማፀናት ገና ባልሰማችውና ባላወቀችው ቀላል ነገር መስሏት እሽ፡፡አሁን ተነስ ብላ ካስነሳችው በኋላ፤ ምንድ ነው እሱ የቸገረህ"? አለችው፡፡ ተነስቶ ወደ ነበረበት የብሩጩማ ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡ አሁንም ከየት መጀመር እንዳለበት ግራ ቢገባውም መንፈሱ ብትጨነቅም ሚስጥሩን ለአበበች ካላካፈለ መፍትሄ ስለማያገኝ ደፍሮ መናገርና መተንፈስ አለበት፡፡ ራሱን አፅናንቶ ለመናገር ወሰነ፡፡
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
==================

ሰሎሜ አላዛር ሱቅ መስራት ከጀመረች ከከስድስት ወር በኃላ
እለቱ ሰኞ ነው፡፡የሳምንቱ መጀመሪያ፡፡አላዛር ድንገት ተከሰተና ሱቁን ዘግተው እንዲወጡ አደረገ፡፡ቀጥታ ወደ መዝናኛ ቦታ ወስዳት፡፡ሲዝናኑ አመሹና አረፍ ብለው እየተጫወቱ ሳለ፡፡
‹‹አንድ ሰዓት ሆነ እኮ ወደቤት አንሄድም እንዴ?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ወደቤት ስትይ?››
‹‹እንዴ ምኑ ነው ያልገባህ…?ወደየቤታችን ነዋ!!››
‹‹ቤት እንደገዛው ነግሬሻለሁ አይደል?››አላት
‹‹አዎ..በጣም ደስ ብሎኛል..በአጭር ጊዜ ስኬታማ እየሆንክ ነው..ጠንካራ ሰራተኛ ስለሆንክ ይገባሀል፡፡››
‹‹አይ ጠንካራ ሰራተኛ ስለሆንኩ ብቻ አይደለም የተሳካልኝ..እድለኛም ጭምር ስለሆንኩ ነው፡፡አያቴ ያወረሰቺኝ ገንዘብ …ቀላል አልጠቀመኝም..ይሄንን የኮንስትራክሽን ስራ ከጀመርኩ በኃላ ደግሞ አሪፍ የተባሉ ሶስት ፕሮጀክቶችን አገኘሁ…ረጅም አመት በስራው የቆዩ ኮንትራክተሮች እንኳን ይሄንን ያህል ስራ በቀላሉ አያገኙም፡፡››
‹‹ቢሆንም ያገኙትን እድልም በስርአት መጠቀምና ውጤታማ መሆንም እኮ ትልቅ የጥንካሬ ምልክት ነው፡፡››
‹‹እዛ ላይ እንኳን ትክክል ነሽ…ያገኘሁትን እድል ላለማባከን የተቻለኝን ሁሉ ከማድረግ አልሰንፍም››አላት በእርግጠኝነት፡፡
‹‹አዎ…ታዲያ እቤቱን መች ነው የምታሳየን?››
‹‹አሁን ጥቂት የሚስተካከሉ ነገሮች ስላሉ እያሳደስኩት ነው…እንዳለቀ ወስጄ አሳይሻለሁ››ሲል ቃል ገባላት፡፡
‹‹እና ሲያልቅ ጎረቤታችንን ልናጣ ነዋ፡፡››አለችው
‹‹ማለት?››
‹‹ያው ኮንደሚኒዬሙን ለቀህ ..አዲሱ ቤትህ ስትገባ ጓረቤት መሆናችን ይቀራል ማለቴ ነው››
‹‹አይ ..እንደዛ እንኳን አላደርግም..እሺ ካልሺኝ አብረን እንገባበታለን…ካልሆነም እሱን አከራይቼ እዛው ጎረቤትሽ ሆኜ መኖሬን ቀጥላለሁ፡፡››ብሎ ያልጠበቀችውን ነገር ነገራት፡፡
‹‹አልገባኝም…እኔ ደግሞ ለምንድነው አብሬህ የምገባው?››
‹‹አንድ ወንድና ሴት አንድ የጋራ ቤት ውስጥ ለምንድነው አብረው የሚገቡት?››ሲል መልሶ ጠየቃት፡፡
‹‹ቆይ ቆይ…..እየጀነጀንከኝ ነው እንዴ?››
‹‹ከተሳካልኝ አዎ››
‹‹ይገርማል ከዚህ ሁሉ አመት መጓተት በኃላ ድንገት ምን ተፈጠረ?››
ወደልቡ በሌባ ጣቱ  እየጠቆመ ‹‹ሁሌም ሀሳቡ እዚህ ውስጥ ነበር ..ልዩነቱ አሁን ከአንደበቴ ምውጣቱ ነው››አላት፡፡
‹‹ቀልድ ጨምርሀል…ባይሆን አንዷን ጥበስና ደግሼ ልዳርህ!››
‹‹አይ ይቅርብኝ ..እኔ አንቺን ማግባት ካልቻልኩ እስከወዲያኛው መመልኮስ ነው የምፈልገው፡፡››
በድንጋጤ አፏን በመክፈት አፍጥጣ አየችው›‹‹እየቀለድክብኝ ነው እንዴ?››
‹‹አረ የምሬን ነው››
‹‹እኔን ጓደኛህን ማግባት ትፈልጋለህ?››
‹‹አዎ በደንብ፡፡››
‹‹ለምን? ››
‹‹ስለማፈቅርሽ ነዋ!!››
‹‹ከመቼ ጀምሮ››
‹‹እኔ እንጃ …ነፍስ ካወቅኩበት ጊዜ ጀመሮ አንቺን እንደማፈቅቅር ነው የማውቀው››
‹‹ይሄኔ ነው መሸሽ….እና እስከዛሬ ለምን ሳትነግረኝ?››
‹‹ስለምፈራሽ..ዛሬ እራሱ እንዴት እንደነገርኩሽ አላውቅም…››
ዝም አለችው…ምን እንደምትለው ምንም ሀሳብ አልመጣላትም..አስባበት ስለማታውቅ በእሷ በኩል ለእሱ ተመሳሳይ ስሜት ይኑራት ወይስ አይኑራት ማወቅ አልቻለችም፡፡
‹‹በል… አሁን ተነስ እንሂድ፡፡››
‹‹እሺ›› ብሎ …ከተቀመጠበት ተነሳ ና ተከተላት፡፡
ለሶስት ወር ያህል በጉዳዩ ላይ መልሰው በማንሳት አልተነጋሩበትም ነበር…
ከሶስት ወር በኃላ ሱቅ ስራ ላይ እያለች ስምንት ሰዓት ላይ መጣና ‹‹ሱቁን እንዝጋውና ..የሆነ ቦታ እንሄዳለን››አላት፡፡
‹‹የት?››
‹‹ሰርፕራይዝ ነው፡፡››
ተስማማችና ሱቁን አብረው ዘጋግዘው  በፒካፕ መኪናው ተያይዘው ሄዱ…ወደ ላፍቶ ነው የወሰዳት ፡፡አዲስ የገዛው አፓርታማ ቤት ውስጥ ነው ይዞት የገባው……ሙሉ ዕቃው የተሞላ እጅግ ውብ ቤት ነበር፡፡
‹‹ይሄ የእኔ ቤት ነው እንዳትለኝ?››አለችው በመደነቅ ፈዛ፡፡
‹‹አይ የእኔ አይደለም የእኛ ቤት ነው፡፡››
‹‹በጣም እኮ ነው የሚያምረው፡፡››
‹‹ስለወደድሽው ደስ ብሎኛል፡፡››
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ ..?እንዴት ላልወደው እችላለሁ? ቤተ መንግስት እኮ ነው የሚመስለው፡፡››
‹‹እንግዲህ እንዳልሺው ቤተ መንግስት ከሆነ ንግስት ይፈልጋል ማለት ነው፡፡››
‹‹እሱን ጫወታ ለጊዜው ትተን ሁሉንም ክፍል እየዞርን እንየው፡፡››
‹‹ይቻላል››ብሎ እየመራ ወደፎቁ ይዞት ወጣ፡፡ንግግሩን ጠንከር ብላ ስላልተቃወመችው ደስ ብሎታል፡፡ፈፅሞ ጥያቄው  እስከወዲያኛው ላለመቀበል ወስና ቢሆን ኖሮ ቁርጥ አድርጋ ምንም አንደበቷን ሳያደናቅፋት ‹‹አይሆንም ››ትለው ነበር፡፡አሁን ግን …ለጊዜው  እንተወው ››ነው ያለችው፡፡
//
እቤቱን ወስዶ ካስጎበኛት ከ15 ቀን በኃላ ድንገት‹‹በሚቀጥለው ሳምንት እቴቴ ጋር ሽማግሌ ልልክ ነው››ብሎ አስደነገጣት፡፡
‹‹ምን?››
‹‹አዎ …ሽማግሎዎችን አነጋግሬ አዘጋጅቼዋለሁ..በኃላ አዲስ እንዳይሆንብሽ ብዬ ነው አሁን የነገርሽው፡፡››
‹‹ያምሀል እንዴ…?እኔ መች እሺ አልኩህና ነው ሽማግሌ የምትልከው?፡፡››
‹‹ችግር የለውም…ሽማግሌ እልካለሁ…የማትፈልጊ ከሆነ ከእናትሽ ተማክረሽ ለሽማግሌዎች አይ አልፈልገውም ማለት ትቺያለሽ፡፡››
‹‹እንደዛ ብል እና በሽማጊሌዎች ፊት መዋረድ አይሆንብህም››
‹‹ግድ የለኝም….ዋናው አንቺን ለማግኘት ከልቤ መሞከሬ ነው፡፡››
‹‹ከዛ በኃላ ግን እዚህ  መስራት አልችልም…››
‹‹እ ..እሱን በተመለከት በውሳኔሽ ተፅእኖ እንዳያሳድርብስሽ ስለፈለኩ ቅድመ ዝግጅት አድርጌለሁ፡፡››
‹‹የምን ቅድመ ዝግጅት?››
ፊት ለፊቱ ያለውን አጀንዳ አንሳና…‹‹ይሄንን ዝርዘር ተመልከችው..እዚህ ሱቅ ውስጥ ያለው እቃ  ነው፡፡ይሄ ደግሞ ውል ነው..ይሄንን ሱቅ ከአሁን ወዲያ አልፈልገውም….ሁሉንም ዕቃ ትረከቢኝና ቀስ እያልሽ በሁለት አመት ውስጥ ትከፍይኛለሽ…ይሄ ማለት ይሄንን ውል ከፈረምሽ በኃለ የእኔ ሰራተኛ አይደለሽም ማለት ነው፡፡የራስሽን ንግድ ፍቃድ አውጥተሸ በራስሽ መስራት ትቀጥያለሽ ማለት ነው፡፡እናም ያ ማለት እንደከዚህ ቀደሙ በፈለኩ ጊዜ ወደሱቅሽ ዘው ብሎ መምጣትና ወደውስጥ ዘልቆ መግባት አልችልም ማለት ነው….እና ሽማግሌዎች ሲመጡ አሺ አገባዋለሁ ብትይም አላገባውም ብለሽ ብትነግሪያቸውም፤ከዚህ ሱቅና ከስራሽ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡በይ ቸው››ብሏት ጥሎት ወጥቶ ሄደ፡፡
እንዳለው በሳምንቱ ሽማግሌ ላከ ….በሚቀጥለው እሁድ ተመልሰው እንዲመጡና መልሳቸውን የዛን ጊዜ እንደሚያገኙ ተነገራቸው፡፡የሰሎሜ እናት እቴቴ አንድ ብቸኛ ልጇን አስቀምጣ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ልጄ ለመሆኑ ከአላዛር ጋ መቼ ነው የጀመራችሁት?››
‹‹ምንድነው የጀመርነው?››
‹‹ሽማጊሌ ልኮ እያየሽ ምን ትይኛለሽ እንዴ?››
‹‹አይ እቴቴ..እንደሚወደኝ ነገረኝ እንጂ ምንም የጀመርነው ነገር የለም …መልስ እንኳን አልሰጠሁትም፡፡››
‹‹ለምን?››
‹‹እኔ እንጃ እያሰብኩበት ነበር፡፡››
‹‹ምንድነው የምታስቢው…አትወጂውም?››
‹‹እኔ እንጃ… የምወደው ይመስለኛል፡፡››
‹‹አዎ ..እኔም ምትወጂው ይመስለኛል፡፡››
ሰሎሜ በእናቷ ንግግር ተገርማ‹‹እንዴት የምወደው ሊመስልሽ ቻለ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ባትወጂውና ባትፈልጊው ኖሮ ወዲያውኑ ነበር አልፈልግም ብለሽ መልስ ምትሰጪው….እንደሚወድሽ ከነገረሽ ቀን አንስቶ እስከዛሬ ጉዳዩን እያብላላሽውና  እያሰብሽበት ከሆነ ሌላ ምንም ትርጉም ልሰጠው አልችልም፡፡››
#አላገባህም


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////
ሚካኤል ከወህኒ ቤት እንደመጣ ቀጥታ ወደሰፈር ነው ያመራው፡፡ወደቤት ሲገባ አዲስ አለም ከልጇ ጋር እየተዳረቀች ሳሎን ውስጥ ቢያገኛትም ማንኛቸውንም ምንም ሳያናግር ቀጥታ ወደመኝታ ቤት ነበር የተንደረደረው፡፡

‹‹ሚኪ…ምን ሆነሀል.?.ዛሬ ደግሞ ሰላምታ የለም እንዴ?››

‹‹መጣሁ..››ብሎ ብቻ  ወደመኝታ ቤት ገባ…አባቱ የነገሩትን ፎቶ ከግድግዳ ላይ አነሳ ..ከግድግዳው ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ነው…በቀላሉ በእጅ የሚፈረከስ አይነት አይደለም…ከእንደገና ተነደርድሮ ወጣና በጓሮ በኩል ወደ ገራጅ በመሄድ መዶሻ እና መሮ  ይዞ መጣ….‹‹አዲስ አለም ቅዱስን ከወለሉ ላይ አንስታ አቀፈችውና ወደመኝታ ቤቱ ተንቀሳቀሰች…እሷ ከመድረሷ በፊት ሚካኤል ወደውስጥ ገብቶ ከውስጥ ዘጋባት

‹‹እንዴ ሚኪ….ምን እየሆንክ ነው…?ለምንድነው የምትዘጋብን?››

‹‹አዲስ..እባክሽ ጥቂት ደቂቃዎችን ስጪኝ……››ብሎ መሮውንና መዶሻውን በመጠቀም  ግድግዳውን መቆርቆር ጀመረ…ግድግዳ ውስጥ የተቀመጠውን የአባቱን ሚስጥራዊ እቃ ለማግኘት 3 ደቃቃ ያህል ፈጀበት…በላስቲክ በስነሰርአት የተጠቀለለ ነው፡፡አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠና የላስቲኩን እሽግ ፈቶ አልጋው ላይ ዘረገፈው፡፡….አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች አንድ ሜሞሪ ካርድ  ..አንድ ደብዳቤ ነው፡፡፡

መጀመሪያ ፎቶዎቹን አነሳና ተራ በተራ መመልከት ጀመረ…የመጀመሪያው ፎቶ ላይ  አናትዬው የሆነ ሰው ክንድ ላይ ተደግፋ በፈገግታ ስትፍለቀለቅ ይታያል..ጭንቅላቱን የሆነ መርፌ ነገር ጠቅ አደረገው….ይሄ ሰው በህይወት ዘመኑ አይቶት አያውቅም…የእናቱን ዘመዶች ሁሉንም ያውቃል…ታዲያ ይሄ ማን ነው?፡፡ሁለተኛውን ፎቶ  ገለጠና ተመለከተ…እናትዬው እነሱን ከመውለዷ በፊት ገና ጨቅላ ወጣት ሆና የተነሳቸው ፎቶ ነው..ግን አሁንም ያው ሰው አንገቷ ላይ ተጠምጥሞ በፍቅር ጉንጯን ሲስማት ይታያል…ፎቶውን ገለበጠው…ልቅም ባለ የእጅ ፅሁፍ በአንድ መስመር የተፃፈ ፅሁፍ አለ ‹‹ንጥፍ ወርቅ ፍቅሬ በጣም አፈቅርሻለው….ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡››ይላል፡፡
ሁሉንም ፎቶዎች በየተራ እየገለባበጠ ተመለከተው…ተመሳሳይ የሁለቱ ፎቶ ነው…ሲላፉ ሲሳሳሙ….ሲጎራረሱ የተነሱት ፎቶ ነው፡፡
ቤታቸው የወላጆቻቸውን ትዝታ የሚዘክሩ ሁለት ግዙፍ የፎቶ አልበሞች እዳሉ ያውቃል….እናትና እህቱ በአሰቃቂ ሁኔታ ከሞቱ በኃላ በጣም ሲከፋውና ትዝ ሲሉት ለብቻው ክፍል ዘግቶ ተደብቆ  ይመለከት ነበር፡፡እና እዛ አልበም ውሰጥ ዘጠና ፐርሰንት ፎቶ የእሱና የእህትና ወንድሙ ፎቶዎች ፤የበዓል ዝግጅት ፤ የህፃናቱ የልደት በዓል ማስታወሻ ናቸው የሞሉት..እናትና አባቱ በልጆቹ የደስታ ድባብ ውስጥ እንደድምቀት እዚህም እዛም ጣል ተደርገው የተነሱት ነው እንጂ እንዲህ እናቱ ከሌላው ሰውዬ ጋር እንዳደረገችው አይነት አማላይ ፎቶዎች ተነስተው አላየም፡፡

ፎቶውን አስቀመጠና ወረቀቱን አንስቶ አነበበው…
ይድረስ ለምወድሽ ፍቅሬ ንጥፍ ወርቅ …
ይህንን ደብዳቤ ስፅፍልሽ ከአይኖቼ እንባ ሳይሆን ደም እያፈሰስኩ ነው፡፡  ታውቂያለሽ እኔ ከኤለመንተሪ ጀምሮ በጣም ነው የማፈቅርሽ..አንቺም እንደምታፈቅሪኝ አውቃለው፡፡ብዙ አቅድና ብዙ ፕሮግራም ነበረን፡፡በቅርብም ለመጋባት ተነጋግረንና ተማምለን ነበር፡፡አሁን ግን ያንን ቃሌን ማክበር አልችልም፡፡አባዬ ምን ያህል ኃይለኛ እና ጥብቅ ሰው እንደሆነ ታውቂያለሽ  ..አሁን አሜሪካ ካለው ወንድሙ ጋር ተነጋግሮ አሜሪካ እንድሄድ ወስኖ ሁሉም ፕሮሰሶች ጨርሶ ሊልከኛ ነው…ማለቴ… አሁን ይሄ ደብዳቤ ሲደርስሽ ምን አልባት እኔ በርሬም ሊሆን ይችላል፡፡

ይቅር በይኛ…..ያንቺው  ለሚ በቀለ፡፡ይላል
እዛ ደብዳቤ ላይ ብዙ የተንጠባጠቡ የእንባ ጠብታዎች ይታያሉ፡፡ሚካኤል ያየውም ሆነ ያነበበው ነገር  ምንም እየገባው አይደለም..ከውጭ ደግሞ አዲስአለም የመኝታ ቤቱን በራፍ እየቆረቆረች እየረበሸችው ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ሄዶ በራፉን ከፈተ፡፡ በራፉ ላይ ልጇን አቅፋ ተገተትራ በድንጋጤ በድን የሆነችውን አዲስ አለም ላይ አፈጠጠባት፡፡

‹‹አዲስ ምንድነው?››

‹‹እንዴት መኝታ ቤቱን በላይህ ላይ ዘግተህ ምን እያደረክ ነው?››በስጋትና በፍራቻ ተወጥራ ጠየቀችው፡፡

‹‹ኡፍ …ስራ ይዣለሁ ስልሽ አትሰሚም…..ባክሽ አትረብሺኝ››በማለት አንቧረቀና መልሶ ዘጋባት፡፡ከዛ  ወደአልጋው ተመለሰ፡፡አዲስአለም በመጀመሪያ ከደነገጠችውን  በላይ ደነገጠች…ሚካኤል ምንም ባልገባት ነገር እንዲህ አመናጭቋት አያውቅም፡፡

ወደሳሎን ተመለሰችና ፀአዳ ጋር ደወለችላት፡፡
ስታወራ ድምፃ ይንቀጠቀጣል‹‹ሄሎ ፀዲ..አሁኑኑ ወደቤት ነይ››
‹‹እንዴ ምን ሆንሽ..?

ቅዱስ አመመው እንዴ?››
‹‹አይደለም..አባትዬው ነው፡፡››

ፀአዳ በጣም ደነገጠች‹‹እንዴ  ሚኪ ምን ሆነ?››

‹‹እኔ እንጃለት… ቅድም አንቺ ጋር የመጣሁ ጊዜ አባቱን ለመጠየቅ ወህኒ ቤት ሄዶ ነበር…ከዛ ሲመለስ እንደእብድ አድርጎት መኝታ ቤቱ ገባ..ከዛ ወጣና መዶሻና መሮ ይዞ ገብቶ በራፉን ከውስጥ በመዝጋት ግድግዳውን ሲነድለው ነበር…አንኳኩቼ ምን እንደሆነ ስጠይቀው አጓርቶብኝ መልሶ ዘጋው…እህቴ ቶሎ ድረሺኝ…የቀትር ጂኒ ሳያጠናግረው አይቀርም››

‹‹ስለአባቱ መጥፎ ነገር ሰምቶ ይሆን እንዴ?››

‹‹መሰለኝ….ወይ በፈጣሪ ምን አልባት እዛ ሲደርሰ ገድለዋቸው እንዳይሆን ነው የምፈራው..እንደዛ ቢሆንስ በራፍ አስዘግቶ ግድግዳ ያስንዳል እንዴ…?››

‹‹በቃ መጣሁ ..እስከዛው ተረጋጊ››አለቻትና ስልኩን ከመዝጋቷ በፊት ቦርሳውን አንጠለጠለችና መንገድ ጀመረች፡፡

ሚካኤል ሜሞሪውን አነሳና ስልኩ ውስጥ ከተተው፡፡ሁለት ፎልደሮች  አሉት፡፡አንደኛውን ከፈተ ….በምስሉ በቅድሚያ ምትታየው እናቱ ነች፡፡አዎ ቡቲክ ቤታቸው ውስጥ ሆና ልብሶችን ሰታስተካከል ይታያል…ወዲያው አንድ በእሷ እድሜ ያለ ሰው  መጣ …የሰውዬው ጀርባው ነው ሚታዬው እናትዬው ግን በሰውዬው መምጣት ስትደነግጥ ይታያል፡፡

‹‹ለሚ እንዴት መጣህ?››አገላብጣ እየሰማችው ትጠይቀዋለች፡፡

‹‹እንዴት መጣህ ነው እንኳን ደህና መጣህ ነው የሚባለው?እዚህ ስብሰባ ነበረን …ሳላይሽ ተመልሼ መሄድ አልቻልኩም›››

‹‹እንዴ ከሶስት ቀን በኃላ ቀጠሮ ነበረን እኮ…››

‹‹እሱም እንዳለ ነው…ግን እኔ እኮ በየቀኑ ላገኝሽ ነው የምፈልገው…እንደውም ሙሉ በሙሉ የእኔ እንድትሆኚ ነው የምፈልገው፡፡››

‹‹እሱንማ አስረግዘኘኝ  ጥለኸኝ አሜሪካ ከመሄድህ በፊት   ማሰብ ነበረብህ፡፡››

‹‹ይሄንን እኮ ብዙ ጊዜ  ተነጋግረንበት  ሁኔታውን አስረድቼሽ ይቅር ብለሽኛል..አይደል እንዴ የእኔ ፍቅር?››

‹‹አዎ ግን …ይቅር አልኩህ ማለት ለአመታት የገነባሁት ትዳሬንና ልጆቼን በትኜ ወደአንተ ለመመለስ እፈልጋለው ማለት አይደለም፡፡››

‹‹ልጆችሽን በትኚ አልልኩም እኮ ….ባልሽን ፍቺና ልጆቹን ይዘሽ ነይ ነው፡፡›››

‹‹አይ ያንን ሳደርግ ቅጣው እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ይመስልሀል….?እሱ ምንም እንከን የማይወጣለት ድንቅ አባትና ምርጥ ባል ነው፡፡ልጆቹን እንዴት እንደሚወድ እና እንዴት እንደሚንከባከብ ብታውቅ እንዲህ ለማለት አትደፍርም..በተለይ ትርሲትን በልዩ ሁኔታ ነው የሚወዳት…ሲጠራት እኮ እናቴ ነው የሚላት…እሷስ ብትል..?››

‹‹ግን እውነተኛ ልጁ አይደለችም…ትርሲት የእኔ  ልጅ ነች፡፡››

ሚካኤል በሚሰማው ነገር ሆዱ ሲገለባበጥ ይታወቀዋል…አረ እንደውም ሊያስታውከው እየተናነቀው ነው፡፡

‹‹አረ ድምጽህን ቀንስ..ድንገት ሰው ቢሰማህስ?››