#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
////
ፀአዳ የ21 ዓመት አዋቂ ሴት ነች፡፡አገላለጹ ይጋጫል አይደል?የ22 አመት ወጣት ሆኖ አወቂ ሴት ነች ሲባል ፡፡አዎ እሷ የ15 አመት እና የ9 ኛ ክፍል ተማሪ እያለች ድብን ያለ ፍቅር ያዟት ነበር፡፡በ16 ዓመት የልደት በአሏ በሚከበርት ቀን በወቅቱ የ19 ዓመት ጎረምሳና የ11 ክፍል ተማሪ ለነበረው የልቧ ሰው በፍደኝነት ድንግልናዋን አስረከበች፡፡ከሁለት ወር በኃላ ማርገዟን አወቀች… ነገረችው፡፡ከሳምንት በኃላ እሷን ሳይሰነበታት.. ደግሞ ሳይስማት…ደግሞ ቀሚስሽን ላውልቅ ፤ ጡትሽን ልጥባ ሳይላት እሷንም ሆነ ከተማዋን ጥሎ ውትድርና ተቀጥሮ ሄደ…ያንን የመሰለ አስቀያሚ ዜና የሰሚ ሰሚ ከሰው ነው የሰማችው፡፡ያንን የሰማች ቀን ሰማይ ምድሩ ነበር የዞረባት፡ያልጠና ጮርቃ ልቧ ስንጥቅጥቅ አለ….ደነዘዘች…… ፡፡በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ማርገዞን አወቀች…ሰማይ ምድሩ ዞረባት…እና በወቅቱ ሁለት ምርጫ ነበር የታያት ..አንድም በሆነ ዘዴ መርዝ በመጠጠት ወይም በገመድ ተንጠልጥሎ ብቻ በሆነ ዘዴ እራሷን ማጥፋት ሲሆን ፤ ሁለተኛው ደግሞ ብን ብላ ሀገሯን ጥላ ወደማታውቀው ሀገር ሄዳ ህይወት እንዳደረጋቻት መሆን፡፡
….በምን አሳማኝ ምክንያት እንደሆነ ባታውቅም ሁለተኛውን መረጠችና ከተወለደችበትና ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ከሚኖርበት ዶዶላ ከተማ በአንድ አነስተኛ ሻንጣ ልብሷና እና ይጠቅሙኛል ያለችውን ዶክመንት ይዛ ወደአዳማ የሚሄድ መኪና ውስጥ ተሳፈረች፡፡እንግዲህ የህይወት ዘመን ባለውለታዋን የሆነውን ሚካኤልን የተዋወቀችው እዛ መኪና ላይ ነበር፡፡በወቅቱ አጋጣሚ ሆኖ ጎን ለጎን ነበር የተቀመጡት፡፡የተወሰኑ ቃላቶች እየተለዋወጡ ከተግባቡ በኃላ ድንገት ወዳልታሰበ ቁምነገር ያለው ውይይት ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹አዳማ ነው የምትሄጂው ወይስ ወደአዲስ አበባ ታልፊያለሽ?
››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አላውቅም…››ስትል በደፈናው መለሰችለት፡፡
‹‹አልገባኝም››
‹‹እኔ እንጃ ..ከተመቸኝ አዳማ እቀራለው…ከለበለዚያ ወደአዲስ አበባ ሄዳለው…እድል እንዳደረገቺኝ ነው የምሆነው››
‹‹ማለት …ቤተሰብ ጋር ነው የምትሄጂው?››ጥያቄውን አሻሽሎ ጠየቃት፡፡
‹‹አይደለም…ስራ ፍለጋ ነው የምሄደው››
‹‹ስራ ፍለጋ….ምን አይነት ስራ?››
‹‹የተገኘውን ስራ፡፡››
‹‹ምነው… ቤተሰቦችሽ የት ናቸው?››
‹‹ዶዶላ ነበር የሚኖሩት …ማለት እናቴ ና እኔ ብቻ ነበር..አሁን እናቴ ስለሞተች ብቻዬን ቀረው…እናቴ የሞተችበት ሀገር ደግሞ ተረጋግቼ መኖር አልቻልኩም..ስለዚህ የእድሌን ልሞክር ብዬ ዝም ብዬ ነው እየተጓዝኩ ያለሁት….››ንግግሯን ተከትሎ ከአይኖቾ እንባዋ እየተንከባለለ ፊቷን በማጠብ ወደታች ይወርድ ጀመር፡
የሚካኤል አይኖቸ እንባ አቀረሩ‹‹በጣም አዝናለሁ….አይዞሽ እሺ››
‹‹አረ ችግር የለውም…መኖር ካቃተኝ መሞት አያቅተኝም››ስትል የበለጠ አስደንገጭ ነገር ነገረችው፡፡እሱ ደግሞ እራስን ማጥፋትን በተመለከት እህቱንና እናቱን በቅርብ ያጣ ሰው ስለነበር በቀላሉ ነው ስሜቱ የተነካው፡፡እና በተቻለው መጠን ሊረዳት ወዲያው ነው በውስጡ ውሳኔውን የወሰነው፡፡
‹ኸረ በፍጽም እንደዛ አታስቢ…ቆይ ትምህርት ተምረሻል?››
‹‹አዎ ግን.. ገና ዘጠነኛ ክፍል ነኝ››
‹‹እንግዲያው ለአንቺ የሚሆን ስራ አለኝ››በማለት ያልጠበቀችውን የሚያስፈነጥዝ የምስራች አበሰራት፡፡ማመን አልቻለችም‹‹እየቀለድክብኝ አይደለም አይደል?››
‹‹አይ እውነቴን ነው…አዳማ ላይ ቡቲክ አለኝ…ፍቅረኛዬ ነች የምትሰራው..ግን በቅርብ ትምህርት ስለምትጀምር የሚረዳት ሰው ያስፈልጋታል…እና ሰው ለመቅጠር እያፈላለግን ነበር››
‹‹በጣም ደስ ይለኝ ነበር…ግን ምንም አይነት ተያዥ እኮ የለኝም..ያለኝ መታወቂያ እንኳን የትምህርት ቤት ብቻ ነው››ስትል ስጋቷን ያለምንም መሸፋፈን በግልፅ ነገረችው፡፡
‹‹ችግር የለውም..እኔ ዋስ እሆንሻለው››ሲል ከስጋቷ ገላገላት፡፡
እንባዋን መገደብ ስላልቻለች ለሁለተኛ ጊዜ ማለቀስ ጀመረች..ያሁኑ ለቅሶ ግን የደስታ ነበር፡፡
‹‹ኸረ አታልቅሺ..በፈጣሪ እኔ ሰው ሲያለቅስ ማየት አልፈልግም››ብሎ ከኪሱ ሶፍት አወጣና አቀበላት…..ተቀበለችና ፊቷን ጠረረገችበት፡፡
እንዳለው አዳማ እንደወረዱ ቀጥታ ይዟት ወደ ቤት ሄደ… ወስዶ ከፍቅረኛው ጋር አስተዋወቃት፡፡በመሰራት ላይ ካለው ጅምር ቤቱ አንድ ክፍል ቤት አስተካከለና ዕቃ አሟልቶ አስረከባት፡፡ሰው ሳይሆን መላአክ መስሎ ተሰማት፡፡እሱም ብቻ ሳይሆን ፍቅረኛው አዲስ አለምም በልዩ ሁኔታ እንደጓደኛ ብቻ ሳይሆን እንደታናሽ እህት ተቀብላ ወደደቻት….በዚህም ፀአዳ ለረጅም ወራቷች ስታማርረው የነበረውን ፈጣሪዋን ይቅርታ ጠይቃ ማመስገን ጀመረች፡፡
በዚህ ሁኔታ ነው ሚካኤል እና ፀአዳ የተዋወቁት..፣ከዛ ብዙም ሳትቆይ ከቤተሰብ ጠፍታ የመጣችበትን ትክክለኛ ምክንያት ለሚካኤል እና ለፍቅረኛው ለአዲስአለም ነገረቻቸው…እንደዛ ያደረገችው ሆዷ እየገፋ ሲሄድ የግድ መጋለጧ የማይቀር መሆኑን ስለተገነዘበች ነው፡፡
ከዛ ልጇን በእጇቸው ላይ ወልዳ ከእሷ እኩል እየተንከባከቡ አሳድጉላት፡፡ዛሬ ላይ እነሱም አንድ ቤት ተጠቃለው መኖር ከጀመሩ አራት አመት ያለፋቸውና የሶስት አመት ልጅ ያላቸው ሲሆን በተለያየ ምክንያት በዚህ ወር ይሁን… በሚቀጥለው አመት እያሉ ሲያዘዋወሩት የነበረው ሰርጋቸውን ለመደገስ አሁን ቀን ተቆርጦ በጀት ተመድቦለት እንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ፡፡
እና ፀአዳም ይሄንን የወዳጆቾን ሰርግ ልዩ እና በህይወት ዘመናቸው ሙሉ የሚያስታውሱት እንዲሆን ትፈልጋለች፡፡ለዛ ነው ምንም ነገር እንዳይጎድል ለወራት ቀንና ለሊት እንቅልፍ አጥታ ስትለፋ የሰነበተችው ፡አሁን አንድ ነገር ብቻ ይቀራታል፡፡በዚህ ሰርግ ላይ ለሚካኤል ብቸኛ ዘመድ የሆነውን አንድ ወንድሙን እንደምንም አሳምና ሰርጉ ላይ እንዲገኝ በማድረግ ሰርፕራይዝ በማድረግ ደስታውን ሙሉ ልታደርግለት እቅድ አውጥታለች፡፡ሚካኤል ለረጅም ጊዜ አውርቶትና አግኝቶት የማያውቀው ወንድሙ ዘሚካኤል በሆነ ተአምር በሠርጋቸው ላይ እንዲገኝ ለማድረግ ከልቧ ቆርጣ ተነስታለች።
ይህንን ሀሳብ በአእምሮዋ ስታሰላስልና ስትዘጋጅበት ከወር በላይ ነው የቆየችው፡፡በጣም በብዙ ጥረትና በብዙ ድካም መውጫ መግቢያውን ፕሮግራሞቹንና ልምዶቹን ስታጠና ነበር ሰነበተችው፡፡በቋሚነት በሚኖርበት አዲስአበባ እሱን ለማግኘት ፈተና ነው፡፡ በትክክል እንዴት እሱ በሀሳቧ እንዲስማማ ለማድረግ እንደምትችል እስካአሁን ድረስ በትክክል አላወቀችም።ምክንያቱም ዘሚካኤል እንደማንኛውም ሰው በቀላሉ አግኝተውት የሚያናግሩትና የሚያሳምኑት አይነት ሰው አይደለም፡፡እሱ ሚሊዬኖች የሚያብዱለት ከሀገሪቱ ዝነኛ ድምጻዊያን መካከል ከዋናዎቹ አንደኛው ነው፡፡በዛው ልክ ፕሮግራሞቹ የተጣበቡ..አጃቢዎች የበዙ ሰው ነው፡ቢሆንም ይሄንን ማድረግ አለባት፡፡ይሄ ለምትወዳቸው ና የእድሜ ዘመን ባለውለታዋ ለሆኑት ባልና ሚስቶች እንደስጦታ አድርጋ ልታቀርብላቸው ያሳበችው ትልቅ ስጦታ ነው፡፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
////
ፀአዳ የ21 ዓመት አዋቂ ሴት ነች፡፡አገላለጹ ይጋጫል አይደል?የ22 አመት ወጣት ሆኖ አወቂ ሴት ነች ሲባል ፡፡አዎ እሷ የ15 አመት እና የ9 ኛ ክፍል ተማሪ እያለች ድብን ያለ ፍቅር ያዟት ነበር፡፡በ16 ዓመት የልደት በአሏ በሚከበርት ቀን በወቅቱ የ19 ዓመት ጎረምሳና የ11 ክፍል ተማሪ ለነበረው የልቧ ሰው በፍደኝነት ድንግልናዋን አስረከበች፡፡ከሁለት ወር በኃላ ማርገዟን አወቀች… ነገረችው፡፡ከሳምንት በኃላ እሷን ሳይሰነበታት.. ደግሞ ሳይስማት…ደግሞ ቀሚስሽን ላውልቅ ፤ ጡትሽን ልጥባ ሳይላት እሷንም ሆነ ከተማዋን ጥሎ ውትድርና ተቀጥሮ ሄደ…ያንን የመሰለ አስቀያሚ ዜና የሰሚ ሰሚ ከሰው ነው የሰማችው፡፡ያንን የሰማች ቀን ሰማይ ምድሩ ነበር የዞረባት፡ያልጠና ጮርቃ ልቧ ስንጥቅጥቅ አለ….ደነዘዘች…… ፡፡በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ማርገዞን አወቀች…ሰማይ ምድሩ ዞረባት…እና በወቅቱ ሁለት ምርጫ ነበር የታያት ..አንድም በሆነ ዘዴ መርዝ በመጠጠት ወይም በገመድ ተንጠልጥሎ ብቻ በሆነ ዘዴ እራሷን ማጥፋት ሲሆን ፤ ሁለተኛው ደግሞ ብን ብላ ሀገሯን ጥላ ወደማታውቀው ሀገር ሄዳ ህይወት እንዳደረጋቻት መሆን፡፡
….በምን አሳማኝ ምክንያት እንደሆነ ባታውቅም ሁለተኛውን መረጠችና ከተወለደችበትና ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ከሚኖርበት ዶዶላ ከተማ በአንድ አነስተኛ ሻንጣ ልብሷና እና ይጠቅሙኛል ያለችውን ዶክመንት ይዛ ወደአዳማ የሚሄድ መኪና ውስጥ ተሳፈረች፡፡እንግዲህ የህይወት ዘመን ባለውለታዋን የሆነውን ሚካኤልን የተዋወቀችው እዛ መኪና ላይ ነበር፡፡በወቅቱ አጋጣሚ ሆኖ ጎን ለጎን ነበር የተቀመጡት፡፡የተወሰኑ ቃላቶች እየተለዋወጡ ከተግባቡ በኃላ ድንገት ወዳልታሰበ ቁምነገር ያለው ውይይት ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹አዳማ ነው የምትሄጂው ወይስ ወደአዲስ አበባ ታልፊያለሽ?
››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አላውቅም…››ስትል በደፈናው መለሰችለት፡፡
‹‹አልገባኝም››
‹‹እኔ እንጃ ..ከተመቸኝ አዳማ እቀራለው…ከለበለዚያ ወደአዲስ አበባ ሄዳለው…እድል እንዳደረገቺኝ ነው የምሆነው››
‹‹ማለት …ቤተሰብ ጋር ነው የምትሄጂው?››ጥያቄውን አሻሽሎ ጠየቃት፡፡
‹‹አይደለም…ስራ ፍለጋ ነው የምሄደው››
‹‹ስራ ፍለጋ….ምን አይነት ስራ?››
‹‹የተገኘውን ስራ፡፡››
‹‹ምነው… ቤተሰቦችሽ የት ናቸው?››
‹‹ዶዶላ ነበር የሚኖሩት …ማለት እናቴ ና እኔ ብቻ ነበር..አሁን እናቴ ስለሞተች ብቻዬን ቀረው…እናቴ የሞተችበት ሀገር ደግሞ ተረጋግቼ መኖር አልቻልኩም..ስለዚህ የእድሌን ልሞክር ብዬ ዝም ብዬ ነው እየተጓዝኩ ያለሁት….››ንግግሯን ተከትሎ ከአይኖቾ እንባዋ እየተንከባለለ ፊቷን በማጠብ ወደታች ይወርድ ጀመር፡
የሚካኤል አይኖቸ እንባ አቀረሩ‹‹በጣም አዝናለሁ….አይዞሽ እሺ››
‹‹አረ ችግር የለውም…መኖር ካቃተኝ መሞት አያቅተኝም››ስትል የበለጠ አስደንገጭ ነገር ነገረችው፡፡እሱ ደግሞ እራስን ማጥፋትን በተመለከት እህቱንና እናቱን በቅርብ ያጣ ሰው ስለነበር በቀላሉ ነው ስሜቱ የተነካው፡፡እና በተቻለው መጠን ሊረዳት ወዲያው ነው በውስጡ ውሳኔውን የወሰነው፡፡
‹ኸረ በፍጽም እንደዛ አታስቢ…ቆይ ትምህርት ተምረሻል?››
‹‹አዎ ግን.. ገና ዘጠነኛ ክፍል ነኝ››
‹‹እንግዲያው ለአንቺ የሚሆን ስራ አለኝ››በማለት ያልጠበቀችውን የሚያስፈነጥዝ የምስራች አበሰራት፡፡ማመን አልቻለችም‹‹እየቀለድክብኝ አይደለም አይደል?››
‹‹አይ እውነቴን ነው…አዳማ ላይ ቡቲክ አለኝ…ፍቅረኛዬ ነች የምትሰራው..ግን በቅርብ ትምህርት ስለምትጀምር የሚረዳት ሰው ያስፈልጋታል…እና ሰው ለመቅጠር እያፈላለግን ነበር››
‹‹በጣም ደስ ይለኝ ነበር…ግን ምንም አይነት ተያዥ እኮ የለኝም..ያለኝ መታወቂያ እንኳን የትምህርት ቤት ብቻ ነው››ስትል ስጋቷን ያለምንም መሸፋፈን በግልፅ ነገረችው፡፡
‹‹ችግር የለውም..እኔ ዋስ እሆንሻለው››ሲል ከስጋቷ ገላገላት፡፡
እንባዋን መገደብ ስላልቻለች ለሁለተኛ ጊዜ ማለቀስ ጀመረች..ያሁኑ ለቅሶ ግን የደስታ ነበር፡፡
‹‹ኸረ አታልቅሺ..በፈጣሪ እኔ ሰው ሲያለቅስ ማየት አልፈልግም››ብሎ ከኪሱ ሶፍት አወጣና አቀበላት…..ተቀበለችና ፊቷን ጠረረገችበት፡፡
እንዳለው አዳማ እንደወረዱ ቀጥታ ይዟት ወደ ቤት ሄደ… ወስዶ ከፍቅረኛው ጋር አስተዋወቃት፡፡በመሰራት ላይ ካለው ጅምር ቤቱ አንድ ክፍል ቤት አስተካከለና ዕቃ አሟልቶ አስረከባት፡፡ሰው ሳይሆን መላአክ መስሎ ተሰማት፡፡እሱም ብቻ ሳይሆን ፍቅረኛው አዲስ አለምም በልዩ ሁኔታ እንደጓደኛ ብቻ ሳይሆን እንደታናሽ እህት ተቀብላ ወደደቻት….በዚህም ፀአዳ ለረጅም ወራቷች ስታማርረው የነበረውን ፈጣሪዋን ይቅርታ ጠይቃ ማመስገን ጀመረች፡፡
በዚህ ሁኔታ ነው ሚካኤል እና ፀአዳ የተዋወቁት..፣ከዛ ብዙም ሳትቆይ ከቤተሰብ ጠፍታ የመጣችበትን ትክክለኛ ምክንያት ለሚካኤል እና ለፍቅረኛው ለአዲስአለም ነገረቻቸው…እንደዛ ያደረገችው ሆዷ እየገፋ ሲሄድ የግድ መጋለጧ የማይቀር መሆኑን ስለተገነዘበች ነው፡፡
ከዛ ልጇን በእጇቸው ላይ ወልዳ ከእሷ እኩል እየተንከባከቡ አሳድጉላት፡፡ዛሬ ላይ እነሱም አንድ ቤት ተጠቃለው መኖር ከጀመሩ አራት አመት ያለፋቸውና የሶስት አመት ልጅ ያላቸው ሲሆን በተለያየ ምክንያት በዚህ ወር ይሁን… በሚቀጥለው አመት እያሉ ሲያዘዋወሩት የነበረው ሰርጋቸውን ለመደገስ አሁን ቀን ተቆርጦ በጀት ተመድቦለት እንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ፡፡
እና ፀአዳም ይሄንን የወዳጆቾን ሰርግ ልዩ እና በህይወት ዘመናቸው ሙሉ የሚያስታውሱት እንዲሆን ትፈልጋለች፡፡ለዛ ነው ምንም ነገር እንዳይጎድል ለወራት ቀንና ለሊት እንቅልፍ አጥታ ስትለፋ የሰነበተችው ፡አሁን አንድ ነገር ብቻ ይቀራታል፡፡በዚህ ሰርግ ላይ ለሚካኤል ብቸኛ ዘመድ የሆነውን አንድ ወንድሙን እንደምንም አሳምና ሰርጉ ላይ እንዲገኝ በማድረግ ሰርፕራይዝ በማድረግ ደስታውን ሙሉ ልታደርግለት እቅድ አውጥታለች፡፡ሚካኤል ለረጅም ጊዜ አውርቶትና አግኝቶት የማያውቀው ወንድሙ ዘሚካኤል በሆነ ተአምር በሠርጋቸው ላይ እንዲገኝ ለማድረግ ከልቧ ቆርጣ ተነስታለች።
ይህንን ሀሳብ በአእምሮዋ ስታሰላስልና ስትዘጋጅበት ከወር በላይ ነው የቆየችው፡፡በጣም በብዙ ጥረትና በብዙ ድካም መውጫ መግቢያውን ፕሮግራሞቹንና ልምዶቹን ስታጠና ነበር ሰነበተችው፡፡በቋሚነት በሚኖርበት አዲስአበባ እሱን ለማግኘት ፈተና ነው፡፡ በትክክል እንዴት እሱ በሀሳቧ እንዲስማማ ለማድረግ እንደምትችል እስካአሁን ድረስ በትክክል አላወቀችም።ምክንያቱም ዘሚካኤል እንደማንኛውም ሰው በቀላሉ አግኝተውት የሚያናግሩትና የሚያሳምኑት አይነት ሰው አይደለም፡፡እሱ ሚሊዬኖች የሚያብዱለት ከሀገሪቱ ዝነኛ ድምጻዊያን መካከል ከዋናዎቹ አንደኛው ነው፡፡በዛው ልክ ፕሮግራሞቹ የተጣበቡ..አጃቢዎች የበዙ ሰው ነው፡ቢሆንም ይሄንን ማድረግ አለባት፡፡ይሄ ለምትወዳቸው ና የእድሜ ዘመን ባለውለታዋ ለሆኑት ባልና ሚስቶች እንደስጦታ አድርጋ ልታቀርብላቸው ያሳበችው ትልቅ ስጦታ ነው፡፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
////
‹‹ቆይ ዘሚካኤል የት ነበር የጠፋው?፡፡››
‹‹እናቱና እህቱ የሞቱ ቀን ነው የተሰወረው፡፡ሁለቱ በመልክም ሆነ በአመካከት ፍጹም ተቃራኒ የሆኑት ወንድማማቾች ከከተማ ተያይዘው ወደቤት ሲገቡ ..ሳሎኑ ፍፁም ትርምስምስ ብሎ ያያሉ ..ግራ በመጋባት ወደውስጥ ዘልቀው ሲገቡ እናታቸው ልቧ ላይ ነጭ አብረቅራቂ ቢላዋ ተሰክቷባት ወለሉ ላይ ዝርግትግት ብላ ተኝታለች..አባትዬው ስሯ በደም በተጨማለቀው እጇቻቸው ጭንቅላታቸውን ይዘው ደንዝዘዋል….፡፡
‹‹እንዴ አባዬ ምንድነው..?እናቴን ምን አደረካት?›› ብለው ሲጮሁ ከፊት ለፊት ኮርኒሱን ከደገፈው ብረት ላይ በታሰረ ሲባጎ አንገቷ የታነቀው እህታቸው በድኗ 360 ዲግሪ ሲሽከረከረከር ይመለከታሉ፡፡ሁለቱም ወንድማማቸች ወደእህትዬው እየሮጡና ሁለት እግሮቾን አንድ ላይ ይዘው ወደላይ ከፍ ያደርጎታል….‹‹ቶሎ በል ቢላዋ አምጣና ..ገመድን ቁረጥ…››
.ዘሚካኤል ይንደረደርና እናትዬው ደረት ላይ የተሰካውን ቢላዋ ይነቅልና ወንበር ላይ ቆሞ ገመዱን ይበጥሳል…እህትዬው ተዝለፍልፍ ሚካኤል ተከሻ ላይ ታርፋለች… ቀስ ብለው ወለል ላይ አሳርፈው በፍጥነት አንገቷ ላይ ያለውን ገመድ አላቀው ትንፋሿን ቢያዳምጡም በውስጧ የቀረ ምንም እንጥፍጣፊ እስትንፋስ አልነበረም….ከዛ ዘሚካኤል ቀጥታ እህቱ የተንጠለጠለችበትን ገመድ የቆረጠበትን እና እናቱ የተገደለችበትን ቢላዋ ይዞ ወደአባትዬው ሲንደረደር…ሚካኤል በደመነፈስ ሮጠ ይጠመጥበታል…
‹‹ልቀቀኝ..እናቴንና እህቴን ገድሎ እሱ በህይወት አይኖርም››
‹‹አይሆንም….ስለሆነውን ምንም ምናውቀው ነገር የለም››ሲል ይመልስለታል፡፡
‹‹እንዴት አናውቅም..?አታይም እንዴ …?እጁ በደም ተጨማልቆ……ልቀቀኝ ልግደለው›› ሲል ይጋበዛል፡፡
‹‹አባቴንም ማጣት አልፈልግም››
‹‹እንግዲያው ሁለታችሁንም እገድላችኃለው…››ይለውና ድብድብ ይጀምራሉ…ይሄ ሁሉ ሲሆን አባትዬው ደንዝዘው ከተቀመጡበት ቦታ ንቅንቅ አላሉም ነበር….ወንድማማቾቹ አባቴን ልግደል አትገድልም በሚል ጠብ እርስ በርሳቸው ተቦቅሰውና ተደባድበው ሳይለይላቸው ቤቱ በፖሊስ ይሞላል፡፡
አባትዬ እነሱ ከመድረሳቸው በፊት ስልክ ደውለው ሚስታቸውን እንደገደሉ ነግሮቸው ነበር፡፡ፖሊሶቹ ወንድማማቾቹን አገላግለው ሶስቱንም ወደእስር ቤት ከወሰዷቸው በኃላ ሬሳዎቹን አንሰተው ለምርመራ ወደሆስፒታል ይልካሉ..በማግስቱ አባትዬው ሚስታቸውንም ሆነ ልጃቸውን የገደሉት እራሳቸው እንደሆነ ቃል ስለሰጡ በዛ መሰረት ሁለቱ ልጇች ይፈታሉ፡፡
ከአራት ቀን በኋላ የእናትና እህታቸውን ሬሳ ተረክበው ከቀበሩ በሆላ ዘሚካኤል በከተማው አልታየም፡፡‹‹አንተ ያንን አውሬ ሰውዬ ገድዬ የእናቴንና የእህቴን ደም እንዳልበቀል ያደረከኝ ጠላቴ ነህ..ከእሱ በላይ እጠላሀለው ..እና ደግሞ መቼም ቢሆን ይቅር አልልህም፡፡››የሚል ማስታወሻ ለወንድሙ ጥሎ ነበር የጠፋው፡፡ቆይቶ እንደሰማነው ከጓደኞቹ ጋር በቦረና በኩል ወደኬኒያ ከዛም ወደጣልያን ከተሻገረ በኋላ…በፊትም ልጅ እያለ ጀምሮ ይሞካክረው በነበረው ሙዚቃ ገፋበትና በትምህርትም አሳድጎ ጥሩ ሙዚቀኛ ሆነ ፡፡ለመጀመሪያ ጊዜ በህይወት መኖሩን ያወቅነው የዛሬ 3 አመት የሙዚቃ ክሊፑን ሲለቅ ነው፡፡
….የዛን ጊዜ ሚካኤል የተደሰተው መደሰት ያው አንቺም አብረሺን ስለነበርሽ ታውቂዋለሽ፡፡ከዛ በሀገር ውስጥ በጣም ተቀባይነት ስላገኘ ..ጓዙን ጠቅልሎ ገባ፡፡በሙዚቃ ብቻ ሳይሆን በፊልም ትወና ላይ መስራት ቀጠለ…እንግዲህ ባለፉት አምስት አመታት የገነባውን ስምና ዝና እኩል ነው የምናውቀው፡፡››
‹‹ይገርማል….ግን ከመጣ በኃላ ወንድሙን ለማግኘት አልሞከረም…?››
‹‹ወይ ማግኘት..እኔ አንኳን ላገኘው ሄጄ ስለወንድሙ ሳነሳበት እንዴት እንደተንገሸገሽ እስከዛሬ ሳስበው ይዘገንነኛል..አሁንም ጥላቻው እንዳለ ነው፡፡አልፎ አልፎ በድብቅ እየመጣ የእናቱንና የእህቱን መቃብር እየጎበኘ እንደሚሄድ አውቃለው….በዛው ልክ ስለአባቱም ሆነ ስለወንድሙ ምንም መስማት እንደማይፈልግ እና ቢሞቱም ግድ እንደሌለው አውቃለው፡፡››
‹‹ተይ እንደዛ አትበይ…..››
‹‹ወይ አንቺ ልጅ ስንት ነገር ውስጥ አስገባሺኝ..ስለእሱ ለማወቅ ለምንድነው የፈለግሽው?፡››ስትል ዳግመኛ ጠየቀቻት፡፡
‹‹እንደምንም ብዬ በሰርጋችሁ ላይ እንዲገኝ ለማድረግ አስቤለው››
‹‹ምን?››አዲስአለም ክፉኛ ነው የደነገጠችው፡፡
‹‹ምነው መጥፎ ሀሳብ ነው እንዴ?››
‹‹አረ በፍጹም…ግን የሚሳካ እቅድ አይደለም….››
‹‹ከተሳካልኝስ?››
‹‹ከተሳካልሽማ….ለሚካኤል በሰርግ ላይ ሌላ ሰርግ ደገሽለት ማለት ይሆናል….በፊቱንም ይወድሻል በቃ የዘላለም ባለውለታው ነው የምትሆኚው››
ፀአዳ ‹‹ለማንኛውም ጉዳዩ በእኔና አንቺ መሀከል በሚስጥር ይያዝ …..ሚካኤል ሰምቶ ካልተሳካ ቅር እንዲሰኝ
አልፈልግም፡፡››ስትል አስጠነቀቀቻት፡፡
‹‹አታስቢ እኔም ባሌ በሰርጉ ሰሞን እንዲያዝንብኝ ስለማልፈልግ ..አልነግረውም…ለአንቺ ግን እንዲቀናሽ በቻልኩት መንገድ ሁሉ አግዝሻለው፡፡››
በዚህ ሁኔታ ነበር ከአዲስ አለም ስለዘሚካኤል የተወሰነ ነገር ማወቅ የቻለችው..ከዛ ወደ ሶሻል ሚዲያ ሄደችና እና ስለእሱ የተፃፉ የጋዜጣ አምዶችና በተለያየ ጊዜ የሰጣቸውን ቃለ መጠይቆችን ሰብስባ ማንበብና ማዳመጥ ነው የቀጠለችው…ይሄ ሂደት አንድ ሳምንት ነው የፈጀባት፡፡በዚህ ጊዜ በአምስት አመት ውስጥ ያወጣችውን ሶስት አልበሞችና ፤ከስምንት በላይ ነጠላ ዜማዎችን እየደጋገመች ያደመጠች ሲሆን እሱ የተሳተፈባቸውን ስምንት የሚሆኑ ፊልሞችንም በጽሞና መመልከት ችላለች፡፡
እና በዚህ አንድ ሳምንት ውስጥ ለአመታት የምታውቀው የቅርቧ ሰው እንደሆነ እንዲሰማት አድርጎታል..ያንን ስሜት ግራ አጋቢ ነው፡፡‹አይ በጣም የምወደው ወንድሜ የሚካኤል ወንድም ስለሆነ በእሱ እይን እሱንም ማየት ጀምሬለው ማለት ነው..›ስትል ለራሷ ማብራሪያ መስጠት ብትሞክርም ሊያሳምናት ግን አልቻለም፡፡
ደግሞ ስለሴሰኝነቱ..በየጊዜው ስለሚቀያይራቸው ሞዴል መሳይ ሴቶች፤ ከዝነኛ እንስቶች ጋር ስለሚጀምረው የፍቅር ግንኙነትና ስለመለያየቱ …ከስራው እኩል አንዳንዴም ከስራው በላይ ነው ሚያወራው፡፡እና ለእንደዚህ አይነት ሴት አውል የማይጨበጥ ሙልጭልጭ ወንድ ምን አይነት ስሜት ነው እየተሰማት ያለው….?መልስ የላትም፡፡ግን አሁን ልታገኘውና ልትጋፈጠው ወስናለች..ዝግጅቷንም ጨርሳለች፡፡
///
ፀደይ ባደረገችው ጥናት እና በሰበሰበችው መረጃ መሰረት የሚካኤል መንታ ወንድም የሆነው ዘሚካኤልን ለማናገር አንድ ብቸኛ መንገድ ብቻ እንዳላት ተረድታለች፡፡በሳምንት ሶስት ቀን በሚሰራበት በከተማዋ ታዋቂ ናይት ክለብ ተገኝታ እድሏን መሞከር ፡፡ከእሷ ባህሪ አንጻር እንደዛ አይነት ቦታ ተገኝታ የማታውቀውን ሰው ማናገር በጣም ከባድ የቤት ሰራ ነው፡፡ቢሆንም የግድ ልትወጣው የሚገባ ተግባር እንደሆነ እራሷን አሳምናለች፡፡
ባለፉት ሁለት ቀን ውስጥ የተባለው ናይት ክለብ ውስጥ በውድቅት ለሊት በመገኘት እሱ ሲዘፍን እና በቀበጥ አድናቂዎቹ ሲሞገስና ሲሸለም መመልከት ብትችልም እሱን ተጠግቶ ለማናገር ያደረገችው ሙከራ ግን ሙሉ በሙሉ አልተሳካላትም ነበር፡፡ዛሬ ግን የግድ ሊሳካላት ይገባል..ምከንያቱም ሰርጉ ከአምስት ቀን በኃላ ነው፡፡ዛሬ አግኝታ ካላናገረችው…ወደእዚህ መጥታ ሌላ ሙከራ የምትሞክርበት ሌላ እድል የላትም፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
////
‹‹ቆይ ዘሚካኤል የት ነበር የጠፋው?፡፡››
‹‹እናቱና እህቱ የሞቱ ቀን ነው የተሰወረው፡፡ሁለቱ በመልክም ሆነ በአመካከት ፍጹም ተቃራኒ የሆኑት ወንድማማቾች ከከተማ ተያይዘው ወደቤት ሲገቡ ..ሳሎኑ ፍፁም ትርምስምስ ብሎ ያያሉ ..ግራ በመጋባት ወደውስጥ ዘልቀው ሲገቡ እናታቸው ልቧ ላይ ነጭ አብረቅራቂ ቢላዋ ተሰክቷባት ወለሉ ላይ ዝርግትግት ብላ ተኝታለች..አባትዬው ስሯ በደም በተጨማለቀው እጇቻቸው ጭንቅላታቸውን ይዘው ደንዝዘዋል….፡፡
‹‹እንዴ አባዬ ምንድነው..?እናቴን ምን አደረካት?›› ብለው ሲጮሁ ከፊት ለፊት ኮርኒሱን ከደገፈው ብረት ላይ በታሰረ ሲባጎ አንገቷ የታነቀው እህታቸው በድኗ 360 ዲግሪ ሲሽከረከረከር ይመለከታሉ፡፡ሁለቱም ወንድማማቸች ወደእህትዬው እየሮጡና ሁለት እግሮቾን አንድ ላይ ይዘው ወደላይ ከፍ ያደርጎታል….‹‹ቶሎ በል ቢላዋ አምጣና ..ገመድን ቁረጥ…››
.ዘሚካኤል ይንደረደርና እናትዬው ደረት ላይ የተሰካውን ቢላዋ ይነቅልና ወንበር ላይ ቆሞ ገመዱን ይበጥሳል…እህትዬው ተዝለፍልፍ ሚካኤል ተከሻ ላይ ታርፋለች… ቀስ ብለው ወለል ላይ አሳርፈው በፍጥነት አንገቷ ላይ ያለውን ገመድ አላቀው ትንፋሿን ቢያዳምጡም በውስጧ የቀረ ምንም እንጥፍጣፊ እስትንፋስ አልነበረም….ከዛ ዘሚካኤል ቀጥታ እህቱ የተንጠለጠለችበትን ገመድ የቆረጠበትን እና እናቱ የተገደለችበትን ቢላዋ ይዞ ወደአባትዬው ሲንደረደር…ሚካኤል በደመነፈስ ሮጠ ይጠመጥበታል…
‹‹ልቀቀኝ..እናቴንና እህቴን ገድሎ እሱ በህይወት አይኖርም››
‹‹አይሆንም….ስለሆነውን ምንም ምናውቀው ነገር የለም››ሲል ይመልስለታል፡፡
‹‹እንዴት አናውቅም..?አታይም እንዴ …?እጁ በደም ተጨማልቆ……ልቀቀኝ ልግደለው›› ሲል ይጋበዛል፡፡
‹‹አባቴንም ማጣት አልፈልግም››
‹‹እንግዲያው ሁለታችሁንም እገድላችኃለው…››ይለውና ድብድብ ይጀምራሉ…ይሄ ሁሉ ሲሆን አባትዬው ደንዝዘው ከተቀመጡበት ቦታ ንቅንቅ አላሉም ነበር….ወንድማማቾቹ አባቴን ልግደል አትገድልም በሚል ጠብ እርስ በርሳቸው ተቦቅሰውና ተደባድበው ሳይለይላቸው ቤቱ በፖሊስ ይሞላል፡፡
አባትዬ እነሱ ከመድረሳቸው በፊት ስልክ ደውለው ሚስታቸውን እንደገደሉ ነግሮቸው ነበር፡፡ፖሊሶቹ ወንድማማቾቹን አገላግለው ሶስቱንም ወደእስር ቤት ከወሰዷቸው በኃላ ሬሳዎቹን አንሰተው ለምርመራ ወደሆስፒታል ይልካሉ..በማግስቱ አባትዬው ሚስታቸውንም ሆነ ልጃቸውን የገደሉት እራሳቸው እንደሆነ ቃል ስለሰጡ በዛ መሰረት ሁለቱ ልጇች ይፈታሉ፡፡
ከአራት ቀን በኋላ የእናትና እህታቸውን ሬሳ ተረክበው ከቀበሩ በሆላ ዘሚካኤል በከተማው አልታየም፡፡‹‹አንተ ያንን አውሬ ሰውዬ ገድዬ የእናቴንና የእህቴን ደም እንዳልበቀል ያደረከኝ ጠላቴ ነህ..ከእሱ በላይ እጠላሀለው ..እና ደግሞ መቼም ቢሆን ይቅር አልልህም፡፡››የሚል ማስታወሻ ለወንድሙ ጥሎ ነበር የጠፋው፡፡ቆይቶ እንደሰማነው ከጓደኞቹ ጋር በቦረና በኩል ወደኬኒያ ከዛም ወደጣልያን ከተሻገረ በኋላ…በፊትም ልጅ እያለ ጀምሮ ይሞካክረው በነበረው ሙዚቃ ገፋበትና በትምህርትም አሳድጎ ጥሩ ሙዚቀኛ ሆነ ፡፡ለመጀመሪያ ጊዜ በህይወት መኖሩን ያወቅነው የዛሬ 3 አመት የሙዚቃ ክሊፑን ሲለቅ ነው፡፡
….የዛን ጊዜ ሚካኤል የተደሰተው መደሰት ያው አንቺም አብረሺን ስለነበርሽ ታውቂዋለሽ፡፡ከዛ በሀገር ውስጥ በጣም ተቀባይነት ስላገኘ ..ጓዙን ጠቅልሎ ገባ፡፡በሙዚቃ ብቻ ሳይሆን በፊልም ትወና ላይ መስራት ቀጠለ…እንግዲህ ባለፉት አምስት አመታት የገነባውን ስምና ዝና እኩል ነው የምናውቀው፡፡››
‹‹ይገርማል….ግን ከመጣ በኃላ ወንድሙን ለማግኘት አልሞከረም…?››
‹‹ወይ ማግኘት..እኔ አንኳን ላገኘው ሄጄ ስለወንድሙ ሳነሳበት እንዴት እንደተንገሸገሽ እስከዛሬ ሳስበው ይዘገንነኛል..አሁንም ጥላቻው እንዳለ ነው፡፡አልፎ አልፎ በድብቅ እየመጣ የእናቱንና የእህቱን መቃብር እየጎበኘ እንደሚሄድ አውቃለው….በዛው ልክ ስለአባቱም ሆነ ስለወንድሙ ምንም መስማት እንደማይፈልግ እና ቢሞቱም ግድ እንደሌለው አውቃለው፡፡››
‹‹ተይ እንደዛ አትበይ…..››
‹‹ወይ አንቺ ልጅ ስንት ነገር ውስጥ አስገባሺኝ..ስለእሱ ለማወቅ ለምንድነው የፈለግሽው?፡››ስትል ዳግመኛ ጠየቀቻት፡፡
‹‹እንደምንም ብዬ በሰርጋችሁ ላይ እንዲገኝ ለማድረግ አስቤለው››
‹‹ምን?››አዲስአለም ክፉኛ ነው የደነገጠችው፡፡
‹‹ምነው መጥፎ ሀሳብ ነው እንዴ?››
‹‹አረ በፍጹም…ግን የሚሳካ እቅድ አይደለም….››
‹‹ከተሳካልኝስ?››
‹‹ከተሳካልሽማ….ለሚካኤል በሰርግ ላይ ሌላ ሰርግ ደገሽለት ማለት ይሆናል….በፊቱንም ይወድሻል በቃ የዘላለም ባለውለታው ነው የምትሆኚው››
ፀአዳ ‹‹ለማንኛውም ጉዳዩ በእኔና አንቺ መሀከል በሚስጥር ይያዝ …..ሚካኤል ሰምቶ ካልተሳካ ቅር እንዲሰኝ
አልፈልግም፡፡››ስትል አስጠነቀቀቻት፡፡
‹‹አታስቢ እኔም ባሌ በሰርጉ ሰሞን እንዲያዝንብኝ ስለማልፈልግ ..አልነግረውም…ለአንቺ ግን እንዲቀናሽ በቻልኩት መንገድ ሁሉ አግዝሻለው፡፡››
በዚህ ሁኔታ ነበር ከአዲስ አለም ስለዘሚካኤል የተወሰነ ነገር ማወቅ የቻለችው..ከዛ ወደ ሶሻል ሚዲያ ሄደችና እና ስለእሱ የተፃፉ የጋዜጣ አምዶችና በተለያየ ጊዜ የሰጣቸውን ቃለ መጠይቆችን ሰብስባ ማንበብና ማዳመጥ ነው የቀጠለችው…ይሄ ሂደት አንድ ሳምንት ነው የፈጀባት፡፡በዚህ ጊዜ በአምስት አመት ውስጥ ያወጣችውን ሶስት አልበሞችና ፤ከስምንት በላይ ነጠላ ዜማዎችን እየደጋገመች ያደመጠች ሲሆን እሱ የተሳተፈባቸውን ስምንት የሚሆኑ ፊልሞችንም በጽሞና መመልከት ችላለች፡፡
እና በዚህ አንድ ሳምንት ውስጥ ለአመታት የምታውቀው የቅርቧ ሰው እንደሆነ እንዲሰማት አድርጎታል..ያንን ስሜት ግራ አጋቢ ነው፡፡‹አይ በጣም የምወደው ወንድሜ የሚካኤል ወንድም ስለሆነ በእሱ እይን እሱንም ማየት ጀምሬለው ማለት ነው..›ስትል ለራሷ ማብራሪያ መስጠት ብትሞክርም ሊያሳምናት ግን አልቻለም፡፡
ደግሞ ስለሴሰኝነቱ..በየጊዜው ስለሚቀያይራቸው ሞዴል መሳይ ሴቶች፤ ከዝነኛ እንስቶች ጋር ስለሚጀምረው የፍቅር ግንኙነትና ስለመለያየቱ …ከስራው እኩል አንዳንዴም ከስራው በላይ ነው ሚያወራው፡፡እና ለእንደዚህ አይነት ሴት አውል የማይጨበጥ ሙልጭልጭ ወንድ ምን አይነት ስሜት ነው እየተሰማት ያለው….?መልስ የላትም፡፡ግን አሁን ልታገኘውና ልትጋፈጠው ወስናለች..ዝግጅቷንም ጨርሳለች፡፡
///
ፀደይ ባደረገችው ጥናት እና በሰበሰበችው መረጃ መሰረት የሚካኤል መንታ ወንድም የሆነው ዘሚካኤልን ለማናገር አንድ ብቸኛ መንገድ ብቻ እንዳላት ተረድታለች፡፡በሳምንት ሶስት ቀን በሚሰራበት በከተማዋ ታዋቂ ናይት ክለብ ተገኝታ እድሏን መሞከር ፡፡ከእሷ ባህሪ አንጻር እንደዛ አይነት ቦታ ተገኝታ የማታውቀውን ሰው ማናገር በጣም ከባድ የቤት ሰራ ነው፡፡ቢሆንም የግድ ልትወጣው የሚገባ ተግባር እንደሆነ እራሷን አሳምናለች፡፡
ባለፉት ሁለት ቀን ውስጥ የተባለው ናይት ክለብ ውስጥ በውድቅት ለሊት በመገኘት እሱ ሲዘፍን እና በቀበጥ አድናቂዎቹ ሲሞገስና ሲሸለም መመልከት ብትችልም እሱን ተጠግቶ ለማናገር ያደረገችው ሙከራ ግን ሙሉ በሙሉ አልተሳካላትም ነበር፡፡ዛሬ ግን የግድ ሊሳካላት ይገባል..ምከንያቱም ሰርጉ ከአምስት ቀን በኃላ ነው፡፡ዛሬ አግኝታ ካላናገረችው…ወደእዚህ መጥታ ሌላ ሙከራ የምትሞክርበት ሌላ እድል የላትም፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዘሚካኤል ተገትሮ በቆመበት የክፍሉ መሀከላዊ ስፍራ እንደደነዘዘ ነው፡፡ልጅቱ አስር ለማይሞሉ ደቂቃዎች ብቻ አብራው ብታሳልፍም….ግን ደግሞ ለቀናት ያህል ያቀፋትና ለሳዕታት ሲስማት የቆየ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው…‹‹.ለምን ጉዳይ መጣች ምን ሰርታ ሄደች?››ብሎ ሲያስብ ሳይወድ ፈገግ አለ…ከቆመበት ተንቀሳቀሰና እጁ ላይ ያለውን የሰርግ የጥሪ ካርድ የያዘውን ፖስታ በራፉ አጠገብ በሚገኘው ቆሻሻ ማጠረቀሚያ ቅርጫት ውስጥ ጨምድዶ ወረወረው፡፡
ለዛች ስሟን እንኳን ላልነገረችው ሴት ልጅ እንደነገራት በዚህ አለም ምንም አይነት ወንድም ሆነ ቤተሰብ አያስፈልገውም እና ወደ የትኛውም ሰርግ የመሄድ ፍላጎት የለውም። እንደውም ከተቻለው ስለቤተሰብ በውስጡ የቀረውን እንጥፍጣፊ ትዝታ ከልቡ አሟጦ መሰረዝ ነው ፍላጎቱ፡፡
ከወገብ በላይ ራቁቱን መሆኑን ትዝ ሲለው ወደጠረጴዛው ሄደና ያወለቀውን ልብስ መልሶ ለበሰው..መጀመሪያ እቅዱ ቀጣይ የሙዚቃ ማቅረቢያ ሰዓቱ እስኪደርስ ድረስ ሻወር ገብቶ ከተለቃለቀ በኃላ 30 ወይም 40 ደቂቃ መተኛትና እረፍት መውሰድ ነበር፡፡አሁን ግን ሻወር የመውሰድም ሆነ የመተኛት ፍላጎቱ ከውስጡ በኖ ጠፍቷል…ቀጥታ ሶፋው ላይ ሄደና ተቀመጠ፡፡ፊትለፊት ካለው ጠረጴዛ ላይ ያለውን የውስኪ ጠርሙስ አነሳና ከፍቶ በብርጭቆ ቀድቶ እየተጎነጨ ማሰላሰል ጀመረ….
‹‹ይህቺ ልጅ ምኑን ነክታ እንዴት ስሜቱን ድፍርስርስ አድርጋ እንደሄደች አያውቅም…ወንድሙ ላይ የያዘበት ቂምና የተበሳጨበት ብስጭት አሁንም ትኩስ ነው፡፡
‹‹ግን የዛን ጊዜ ፈቅዶልኝ አባቴን በዛ ቢላዋ ጨቅጭቄ ብገድለው ኖሮስ…?››ሁል ጊዜ እራሱን የሚጠይቀው ጥያቄ ነው፡፡
አዎ ወንድሙ በድብድብ እና በትግል ባያስቆመው ኖሮ እሱም ይሄን ጊዜ የእድሜ ልክ ፍርድ ተፈርዶበት በአባቱ ምትክ እስር ቤት ውስጥ ተቆልፎበት ተስፋ የሌለው ህይወት ይኖር እንደነበረ…እርግጠኛ ነው፡፡
‹‹ታዲያ እኮ ሚካኤል ወንድምህ የእድሜ ልክ ባለውለታህ እንጂ ጠላትህ አይደለም?››አለው አእምሮው፡፡
‹‹ለምን..ያማ እውነት አይደለም….እሱ እኮ እንደዛ ያደረገው እኔን ከመከራ ለማትረፍ አስቦ ሳይሆን ለዛ ጨካኝ እና ገዳይ አባቱ ለማገዝ ፈልጎ ነው››
‹‹አይ እሱ የአንተ አእምሮ አንሻፎ የተረጎመው ትርጉም ነው…እንደዛም ቢሆን እንኳን በዛ ታሪክ ውስጥ ዋናው ተጠቃሚ አንተ ነህ፡፡በወቅቱ ዝም ብሎህ ያሰብከውን እንድታደርግ ቢፈቅድልህ ኖሮ ዛሬ በዚህ ጊዜ ዝነኛው ድምፃዊና ተዋናዩ ዘሚካኤል የለም ነበር…ሀመር መኪና የሚነዳው…የተንጣለለ ውድና ውብ ቪላ ቤት ውስጥ የሚኖረው…ከአደባባይ እስከቤተመንግስት የሚታወቀውና የሚጋበዘው የመገናኛ ብዙሀኖች የዜና ማጣፈጫ የሆነው ዘሚካኤል አይኖርም ነበር፡፡››ሲል እራሱን በራሱ በዝርዝር አስረዳ፡፡
የአእምሮው የእርስ በርስ ጭቅጭቅ ከዚህ በላይ ማስቀጠል አልቻለም..ምክንያቱም በንዴትና በቁጭት አእምሮው ብቻ ሳይሆን መላ ሰውነቱ እየጋለበት ነው፡፡ጠረጴዛው ላይ ያለውን ብርጭቆ አነሳና ጠቀም አድርጎ ተጎነጨለት እና መልሶ አስቀመጠው፡፡
ከዛ ስለሌላ ነገር ለማሰብ ሞከረ ..ግን አሁንም አእምሮውን የሞላችው ያቺ ከደቂቃዎች በፊት ከሰውነቱ ለጥፎ ያቀፋትና ለሁለት ሰከንድ ሲስማት የነበረችው ሴት ነች፡፡‹‹ቆይ ይህቺ ልጅ ምን የተለየ ነገር ቢኖራት ነው ከአእምሮዬ ልትወጣ ያልቻለችው ?››እራሱን ጠየቀ…‹‹ከንፈሯ ላይ አስማት አለ መሰለኝ…››አለና ፈገግ አለ….‹‹ምን አለ ስሟን እና የሞባይል ቁጥሯን ብጠይቃት ኖሮ…?››በጣም ተቆጨ፡፡
ደግሞ እሷም እሱን በምንም አይነት ሁኔታ ደግማ የማግኘት ፍላጎት እንደሌላት በሚያሳይ ሁኔታ ነው የመጣችበትን ጉዳይ ተናግራ የጥሪ ካርድን እጁ ላይ አስቀምጣ ነው ውልቅ ብላ የሄደችው፡፡
‹‹ባለትዳር ትሆን እንዴ?››የሚል ሀሳብ በአእምሮ ብልጭ አለበት፡፡
ሀሳብን መቋጫ ሳያበጅለት በራፉ በስሱ ተቆረቆረ…ብርጭቆ ውስጥ የቀረችውን ውስኪ ጨለጠና ሶፋውን ለቆ ወደበራፉ ሄደ ..ቀጣይ ዝግጅቱን የሚያቀርብበት ጊዜ መድረሱን ለማሳወቅ በራፉን እንደቆረቆሩ ያውቀል..በራፉን ከፍቶ ሲወጣ ንቁ ሆነው የሚጠብቁት ሁለት ወጠምሻ ጋርዶች ከግራና ከቀኝ ከበቡት፡፡ ሁለት እርምጃ ከተራመደ በኃላ የሆነ ነገር ወደኃላ ሳበው…መልሶ ፊቱን ዞረና ወደክፍሉ ተመለሰ….ከውስጥ በኩል ከበራፉ በስተቀኝ ወዳለው የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ባስኬት አጎነበሰና አጣጥፎ የጣለውን የሰርግ ጥሪ ወረቀት አነሳ ፡፡የሱሪ ኋላ ኪስ ውስጥ ጨመረውና መልሶ ወጣ..ለምን እንዲህ እንዳደረገ ቢጠየቅ ምንም አይነት መልስ የለውም …እንዲሁ በደመነፍስ ያደረገው ነገር ነው፡፡
////
አሁን የዘሚካኤል ምስል ከሙሉ አቋሙ ጋር በአእምሯዋ እየተራወጠ ነው፡፡ሁለቱ ወንድማማቾች ከቁመትና ከፀባይ ውጭ በሌላው ነገር በሚያስደንቅ ሁኔታ ይመሳሰላሉ። የሚካኤል ባህሪያት ከዘሚካኤል ትንሽ ደብዘዝ ያሉ ነበሩ እና የዓይኑ ቀለም ንፁህ ፣ ጠንከር ያለ ሰማያዊ ነበረ ፣ ግን ሁለቱም ሰዎች ተመሳሳይ ውብ ፈገግታ፣ ክብ የፊት ቅርፅ እና ሰልካካ አፍንጫ.. ወተት ከመሰሉ ነጫጭ ድርድር ጥርሶች ጋር አላቸው፤››
እየሾፈረች ያለችውን ቪታራ መኪና ኤክስፐረስ መንገድ ውስጥ አስገብታ ወደ አዳማ እያሽከረከረች ሲሆን አሁንም ስለዛ ዘ-ሚካኤል ስለሚባለው ድምጻዊ ነው የምታሰላስለው፡፡ለሊት 8 ሰዓት ላይ ከእሱ ተለይታ እዛው በአቅራቢያው ወደተከራየችው ፕንሲዬን ሄዳ ለመተኛት ብትሞክርም ምንም እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር እንዲሁ ስትበሳጭና ስትገላበጥ ነው ያደረችው፡፡
ስለእሱ ማሰብ የጀመረችው ቀደም ብላ ታሪኩን ከየጋዜጦችና ከዪቲዩብ ቻናሎች እየሰበሰበች በምታዳምጥበት ጊዜ ነው፡፡እርግጥ ታውቀለች በዩቲዩቭ የቀረበ ዜና ሁሉ በተለይ ስለፍቅርና ፃታዊ ግንኙነት የሚነዙት አብዛኞቹ ተመልካች ለማግኘት የታስቡ…በውሸት የሚፈበረኩ እንደሚሆን ታምናለች..ግን ቢሆንም‹‹ እሳት በሌለበት ጭስ አይጨስም….››በማለት ለሰው ስሜት የማይጨነቅ ጋጠወጥ ወሲባም አድርጋ ስላው ነበር፡፡እና ደግሞ ለሊት እንዳየችው አልተሳሳተችም…በዛ ለሊት እዛ ክፍል ውስጥ ሲያገኛት መጀመሪያ ያደረገው ወደራሱ ስቦ ከንፈሯ ላይ መጣበቅ ነው…..ስለዛች ቅፅበት ስታስብ ከንፈሯ ተንቀጠቀጠባት….የሚያበሳጨው ደግሞ ለማንም ሴት ግርማ ሞገሱንና ውበቱን ለመቋቋም አስቸጋሪ የሆነ ሰው መሆኑን በራሷ ማረጋገጧ ነው…ባለፉት ስድስት አመታት በጣም ብዙ ከሆኑ ወንዶች በብዙ የተለያዩ አጋጣሚዎች ሊፈታተኗት ሞክረው ሾልካና አሳስቃ ..አንዳንዱንም ተኮሳትራና አስፈራርታ እራሷን ማትረፍ ችላለች..ከእሱ ጋር ግን በአንድ እይታ ነው ተዝለፍልፋ እቅፉ ውስጥ የወደቀችው፡፡
እንደምንም ከእቅፉ ወጥታ ለማምለጥ ወደበራፉ በምትራመድበት ጊዜ እንኳን ተንደርድሮ መጥቶ እጇን ይዞ ጎትቶ እንዲያስቀራት እና ተሸክሞ ሶፋው ላይ እንዲጥላት በውስጧ እየተመኘች ነበር፡፡ግን በተመሳሳይ ጊዜ እንደዛ በመመኘቷ እራሷን ስትወቅስና ስትራገም ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዘሚካኤል ተገትሮ በቆመበት የክፍሉ መሀከላዊ ስፍራ እንደደነዘዘ ነው፡፡ልጅቱ አስር ለማይሞሉ ደቂቃዎች ብቻ አብራው ብታሳልፍም….ግን ደግሞ ለቀናት ያህል ያቀፋትና ለሳዕታት ሲስማት የቆየ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው…‹‹.ለምን ጉዳይ መጣች ምን ሰርታ ሄደች?››ብሎ ሲያስብ ሳይወድ ፈገግ አለ…ከቆመበት ተንቀሳቀሰና እጁ ላይ ያለውን የሰርግ የጥሪ ካርድ የያዘውን ፖስታ በራፉ አጠገብ በሚገኘው ቆሻሻ ማጠረቀሚያ ቅርጫት ውስጥ ጨምድዶ ወረወረው፡፡
ለዛች ስሟን እንኳን ላልነገረችው ሴት ልጅ እንደነገራት በዚህ አለም ምንም አይነት ወንድም ሆነ ቤተሰብ አያስፈልገውም እና ወደ የትኛውም ሰርግ የመሄድ ፍላጎት የለውም። እንደውም ከተቻለው ስለቤተሰብ በውስጡ የቀረውን እንጥፍጣፊ ትዝታ ከልቡ አሟጦ መሰረዝ ነው ፍላጎቱ፡፡
ከወገብ በላይ ራቁቱን መሆኑን ትዝ ሲለው ወደጠረጴዛው ሄደና ያወለቀውን ልብስ መልሶ ለበሰው..መጀመሪያ እቅዱ ቀጣይ የሙዚቃ ማቅረቢያ ሰዓቱ እስኪደርስ ድረስ ሻወር ገብቶ ከተለቃለቀ በኃላ 30 ወይም 40 ደቂቃ መተኛትና እረፍት መውሰድ ነበር፡፡አሁን ግን ሻወር የመውሰድም ሆነ የመተኛት ፍላጎቱ ከውስጡ በኖ ጠፍቷል…ቀጥታ ሶፋው ላይ ሄደና ተቀመጠ፡፡ፊትለፊት ካለው ጠረጴዛ ላይ ያለውን የውስኪ ጠርሙስ አነሳና ከፍቶ በብርጭቆ ቀድቶ እየተጎነጨ ማሰላሰል ጀመረ….
‹‹ይህቺ ልጅ ምኑን ነክታ እንዴት ስሜቱን ድፍርስርስ አድርጋ እንደሄደች አያውቅም…ወንድሙ ላይ የያዘበት ቂምና የተበሳጨበት ብስጭት አሁንም ትኩስ ነው፡፡
‹‹ግን የዛን ጊዜ ፈቅዶልኝ አባቴን በዛ ቢላዋ ጨቅጭቄ ብገድለው ኖሮስ…?››ሁል ጊዜ እራሱን የሚጠይቀው ጥያቄ ነው፡፡
አዎ ወንድሙ በድብድብ እና በትግል ባያስቆመው ኖሮ እሱም ይሄን ጊዜ የእድሜ ልክ ፍርድ ተፈርዶበት በአባቱ ምትክ እስር ቤት ውስጥ ተቆልፎበት ተስፋ የሌለው ህይወት ይኖር እንደነበረ…እርግጠኛ ነው፡፡
‹‹ታዲያ እኮ ሚካኤል ወንድምህ የእድሜ ልክ ባለውለታህ እንጂ ጠላትህ አይደለም?››አለው አእምሮው፡፡
‹‹ለምን..ያማ እውነት አይደለም….እሱ እኮ እንደዛ ያደረገው እኔን ከመከራ ለማትረፍ አስቦ ሳይሆን ለዛ ጨካኝ እና ገዳይ አባቱ ለማገዝ ፈልጎ ነው››
‹‹አይ እሱ የአንተ አእምሮ አንሻፎ የተረጎመው ትርጉም ነው…እንደዛም ቢሆን እንኳን በዛ ታሪክ ውስጥ ዋናው ተጠቃሚ አንተ ነህ፡፡በወቅቱ ዝም ብሎህ ያሰብከውን እንድታደርግ ቢፈቅድልህ ኖሮ ዛሬ በዚህ ጊዜ ዝነኛው ድምፃዊና ተዋናዩ ዘሚካኤል የለም ነበር…ሀመር መኪና የሚነዳው…የተንጣለለ ውድና ውብ ቪላ ቤት ውስጥ የሚኖረው…ከአደባባይ እስከቤተመንግስት የሚታወቀውና የሚጋበዘው የመገናኛ ብዙሀኖች የዜና ማጣፈጫ የሆነው ዘሚካኤል አይኖርም ነበር፡፡››ሲል እራሱን በራሱ በዝርዝር አስረዳ፡፡
የአእምሮው የእርስ በርስ ጭቅጭቅ ከዚህ በላይ ማስቀጠል አልቻለም..ምክንያቱም በንዴትና በቁጭት አእምሮው ብቻ ሳይሆን መላ ሰውነቱ እየጋለበት ነው፡፡ጠረጴዛው ላይ ያለውን ብርጭቆ አነሳና ጠቀም አድርጎ ተጎነጨለት እና መልሶ አስቀመጠው፡፡
ከዛ ስለሌላ ነገር ለማሰብ ሞከረ ..ግን አሁንም አእምሮውን የሞላችው ያቺ ከደቂቃዎች በፊት ከሰውነቱ ለጥፎ ያቀፋትና ለሁለት ሰከንድ ሲስማት የነበረችው ሴት ነች፡፡‹‹ቆይ ይህቺ ልጅ ምን የተለየ ነገር ቢኖራት ነው ከአእምሮዬ ልትወጣ ያልቻለችው ?››እራሱን ጠየቀ…‹‹ከንፈሯ ላይ አስማት አለ መሰለኝ…››አለና ፈገግ አለ….‹‹ምን አለ ስሟን እና የሞባይል ቁጥሯን ብጠይቃት ኖሮ…?››በጣም ተቆጨ፡፡
ደግሞ እሷም እሱን በምንም አይነት ሁኔታ ደግማ የማግኘት ፍላጎት እንደሌላት በሚያሳይ ሁኔታ ነው የመጣችበትን ጉዳይ ተናግራ የጥሪ ካርድን እጁ ላይ አስቀምጣ ነው ውልቅ ብላ የሄደችው፡፡
‹‹ባለትዳር ትሆን እንዴ?››የሚል ሀሳብ በአእምሮ ብልጭ አለበት፡፡
ሀሳብን መቋጫ ሳያበጅለት በራፉ በስሱ ተቆረቆረ…ብርጭቆ ውስጥ የቀረችውን ውስኪ ጨለጠና ሶፋውን ለቆ ወደበራፉ ሄደ ..ቀጣይ ዝግጅቱን የሚያቀርብበት ጊዜ መድረሱን ለማሳወቅ በራፉን እንደቆረቆሩ ያውቀል..በራፉን ከፍቶ ሲወጣ ንቁ ሆነው የሚጠብቁት ሁለት ወጠምሻ ጋርዶች ከግራና ከቀኝ ከበቡት፡፡ ሁለት እርምጃ ከተራመደ በኃላ የሆነ ነገር ወደኃላ ሳበው…መልሶ ፊቱን ዞረና ወደክፍሉ ተመለሰ….ከውስጥ በኩል ከበራፉ በስተቀኝ ወዳለው የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ባስኬት አጎነበሰና አጣጥፎ የጣለውን የሰርግ ጥሪ ወረቀት አነሳ ፡፡የሱሪ ኋላ ኪስ ውስጥ ጨመረውና መልሶ ወጣ..ለምን እንዲህ እንዳደረገ ቢጠየቅ ምንም አይነት መልስ የለውም …እንዲሁ በደመነፍስ ያደረገው ነገር ነው፡፡
////
አሁን የዘሚካኤል ምስል ከሙሉ አቋሙ ጋር በአእምሯዋ እየተራወጠ ነው፡፡ሁለቱ ወንድማማቾች ከቁመትና ከፀባይ ውጭ በሌላው ነገር በሚያስደንቅ ሁኔታ ይመሳሰላሉ። የሚካኤል ባህሪያት ከዘሚካኤል ትንሽ ደብዘዝ ያሉ ነበሩ እና የዓይኑ ቀለም ንፁህ ፣ ጠንከር ያለ ሰማያዊ ነበረ ፣ ግን ሁለቱም ሰዎች ተመሳሳይ ውብ ፈገግታ፣ ክብ የፊት ቅርፅ እና ሰልካካ አፍንጫ.. ወተት ከመሰሉ ነጫጭ ድርድር ጥርሶች ጋር አላቸው፤››
እየሾፈረች ያለችውን ቪታራ መኪና ኤክስፐረስ መንገድ ውስጥ አስገብታ ወደ አዳማ እያሽከረከረች ሲሆን አሁንም ስለዛ ዘ-ሚካኤል ስለሚባለው ድምጻዊ ነው የምታሰላስለው፡፡ለሊት 8 ሰዓት ላይ ከእሱ ተለይታ እዛው በአቅራቢያው ወደተከራየችው ፕንሲዬን ሄዳ ለመተኛት ብትሞክርም ምንም እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር እንዲሁ ስትበሳጭና ስትገላበጥ ነው ያደረችው፡፡
ስለእሱ ማሰብ የጀመረችው ቀደም ብላ ታሪኩን ከየጋዜጦችና ከዪቲዩብ ቻናሎች እየሰበሰበች በምታዳምጥበት ጊዜ ነው፡፡እርግጥ ታውቀለች በዩቲዩቭ የቀረበ ዜና ሁሉ በተለይ ስለፍቅርና ፃታዊ ግንኙነት የሚነዙት አብዛኞቹ ተመልካች ለማግኘት የታስቡ…በውሸት የሚፈበረኩ እንደሚሆን ታምናለች..ግን ቢሆንም‹‹ እሳት በሌለበት ጭስ አይጨስም….››በማለት ለሰው ስሜት የማይጨነቅ ጋጠወጥ ወሲባም አድርጋ ስላው ነበር፡፡እና ደግሞ ለሊት እንዳየችው አልተሳሳተችም…በዛ ለሊት እዛ ክፍል ውስጥ ሲያገኛት መጀመሪያ ያደረገው ወደራሱ ስቦ ከንፈሯ ላይ መጣበቅ ነው…..ስለዛች ቅፅበት ስታስብ ከንፈሯ ተንቀጠቀጠባት….የሚያበሳጨው ደግሞ ለማንም ሴት ግርማ ሞገሱንና ውበቱን ለመቋቋም አስቸጋሪ የሆነ ሰው መሆኑን በራሷ ማረጋገጧ ነው…ባለፉት ስድስት አመታት በጣም ብዙ ከሆኑ ወንዶች በብዙ የተለያዩ አጋጣሚዎች ሊፈታተኗት ሞክረው ሾልካና አሳስቃ ..አንዳንዱንም ተኮሳትራና አስፈራርታ እራሷን ማትረፍ ችላለች..ከእሱ ጋር ግን በአንድ እይታ ነው ተዝለፍልፋ እቅፉ ውስጥ የወደቀችው፡፡
እንደምንም ከእቅፉ ወጥታ ለማምለጥ ወደበራፉ በምትራመድበት ጊዜ እንኳን ተንደርድሮ መጥቶ እጇን ይዞ ጎትቶ እንዲያስቀራት እና ተሸክሞ ሶፋው ላይ እንዲጥላት በውስጧ እየተመኘች ነበር፡፡ግን በተመሳሳይ ጊዜ እንደዛ በመመኘቷ እራሷን ስትወቅስና ስትራገም ነበር፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ምዕራፍ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹ እንዴት ናችሁ.?.የሴት ወሬ ላይ ነበራችሁ መሰለኝ….በመምጣቴ ምቾት አልተሰማችሁም››አለ፡፡
‹‹እንዴ ባልዬው የሴት ወሬ ደግሞ ምንድነው?››ስትል አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው ወንዷችን ማማት ነዋ››ሲል በፈገግታ መለሰላት፡፡
‹‹አንተ እንደዚህማ አትለንም….በዚህ ፀባይህ ላላገባህ እችላለው…የደገስከው ድግስ ብላሽ እንዳይሆንብህ
ፀአዳ ጣልቃ ገባች‹‹አንቺ እንደዛማ አታስፈራሪውም..እስኪ ልብ ይኑርሽና እምቢ በይው….የልጅ እናቷን ሳይሆን ልጃገረዶችን ነው የማንጋጋለት››ስትል መለሰች፡፡
‹‹አንቺ እስስት ለሁለታችንም እኮ ነው እየተሞገትኩ ያለሁት››
‹‹ያንቺን ሙግት አልፈልግም …ይልቅ ሚካኤል… አንተን እና አዲስአለምን ይቅርታ ልጠይቅህ ፈልጌ ነበር። ››አለችው ኮስተር ብላ፡፡
‹‹ምነው ምን ተፈጠረ?››ሚካኤል ብቻ ሳይሆን አዲስአለምም ያልጠበቀችው ስለነበር ግራ ተጋባች፡፡
‹‹ወንድምህን ዘሚካኤል በሰርጋችሁ ቀን እንዲገኝ ለማድረግ የተቻለኝን ጥሬ ነበር…ግን አልተሳካልኝም፣ አሁን የሚመጣበት ምንም ዕድል የለም።››አለችው፡፡
‹‹ለምን ይቅርታ ትጠይቂያለሽ ? እሱ እንደማይመጣ አስቀድመን እናውቅ ነበር፣››በማለት ሚካኤል ተናገረ፡፡
አሁን ግራ የመጋባቱ ተራ የራሷ የፀዳ ሆነ‹‹ቆይ ለመሞከር እንደሄድኩ ታውቅ ነበር እንዴ?››ስትል በጥርጣሬ ተሞልታ ጠየቀችው፡፡
ፈራ ተባ እያለ በሹክሹክታ‹‹አዎ..አውቅ ነበር››አላት፡፡
ወደአዲስአለም ዞረችና‹‹አንቺ በቃ ሚስጥር የሚባል ነገር አታውቂም..ለዛውም እንዳትነግሪው ብዬ አስጠንቅቄሽ?››
‹‹አንቺ ደግሞ ባልና ሚስት አንድ ሀምሳል አንድ አካል ናቸው ሲባል አልሰማሽም እንዴ? ከገዛ አካሌ ምን ብዬ ነው የምደብቀው?››
‹‹አረ የምትገርሚ ነሽ…ሚኪ ግን በጣም አዝናለው…››
‹‹ምን ያህል እንደሞከርሽና እንደጣርሽ አውቃለው….በእውነት አዲስ በነገረች ቀን እንባ አውጥቼ ነው ያለቀስኩት..ማንም ሰው እዲህ አይነት ነገር ላድርግለህ ብሎኝ አያውቅም ..እህቴ በጣም ነው የምወድሽ …በጣም ነው የማመሰግንሽ››አላት
‹‹እኔም በጣም ነው የምወድህ››አለችና ተንደርድራ ሄዳ ተጠመጠመችበት፡፡እሱም ተቀብሎ አቀፋት፡፡
‹‹እናንተ እኔንም እኮ አስቀናችሁኝ››አለችና ከተቀመጠችበት ሄዳ ሁለቱንም አንድ ላይ አቀፈቻቸው፡፡
///
መድረስ አይቀርም ለአመታት ሲታሰብበት እና ለወራት ሲለፋበት የነበር የሰርግ ቀን ደርሶ አዳራሽ ሙሉ እድምተኞች ሙሽሮቹን አጅቦ ሽር ብትን እያሉ ነው፡፡ ፀአዳ በህይወቷ ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት ደስታና ፈንጠዝያ ተሰምቷት አያውቅም?ከሙሽራዋ ጀርባ ሆና በደመቀ ሁኔታ የሚካሄደውን ስነስርዓት እየተከታተለች ነው፡፡በአዲስ አለም የሰርግ ቀሚስ ላይ ያለው የተራቀቀ ዶቃ በመስታወት ላይ ሲያርፍ በተብረቀረቀ ብርሃን አንጸባርቆ መልሶ ወደውስጥ ሲረጭ ስትመለከት በተረት አለም ውስጥ ስላሉ ልዕልቶች እንድታስብ አደረጋት። የአጋቢውን ፓስተር ድምጽ ላይ ለማተኮር ሞክራለች። እሷ ራሷ የለበሰችው ቀሚስ ልዩ አይነት ስሜት እንዲሰማት አድርጓታል…በህይወቷ መቼ ቀሚስ ለብሳ እንደነበረ አታስታውስም፡፡ ምን አልባት ከቤተሰቦቾ ጠፍታ ከወጣች በኃላ ቀሚስ ጨርሱኑ ለብሳ አታውቅም ይሆናል…ሴት መሆኗ እንዲሰማት አትፈልግም…ጠንካራ ታጋይ ሆና ልጇን ማሳደግና ህይወትና ማሸነፍ ብቻ ነው እቅዷ ..ቀሚስ መልበስ ለስላሳ የሚያደርጋት ይመስላታል…በምን ምክንያት እንደዛ ልታስብ እንደቻለች አታውቅም..ግን ደግሞ ትክክል ነበረች፡፡ ይሄው ዛሬ የተለየ ስሜት እየተሰማት ነው…ሴትነቷ ጎልቶ እየበራ ነው…ይሄ ደግሟ ለሚመለከቷት ሰዎች ብቻ ሳይሆን… ለራሷም በደንብ ታውቋታል፡፡ አዲስአለም የሚካኤልን እጅ በመያዝ አጋቢው ፓስተሩ የሚላትን ጥምረታቸውን የሚያበስሩ ውብ ቃላትን ጥርት ባለ ድምፅ ስትደግም ይሰማል… ።
በመከራህም ሆነ በደስታ ጊዜ… ላልለይህ ቃል እገባለው፡፡
በሀዘንህም ሆነ በደስታህ …ጊዜ ከጎንህ ልሆን ቃል እገባለው፡፡
በጤንነትህም ሆነ በህመምህ ጊዜ …ከጎንህ ላልለይ ቃል እገባልው፡፡
ቀላበቱን አውጥቶ አጠለቀላት እሷም አጠለቀችለት፡፡እርስ በርስ እንዲሳሳሙ ተደረገ….ፀደይ በምታየው ነገር ሁሉ አንሳፋፊ አይነት አስካሪ ስሜት እየተሰማት ነው፡፡
እሷ ከረጅም ጊዜ በፊት ነው በደስታ ማመን ያቆመችው፣ ነገር ግን እዚህ ውብ ቦታ ላይ ሆና አዲስአለም እና ሚካኤል ከዚህች ደቂቃ ጀምሮ ባልና ሚስት መሆናቸውን በፓስተሩ ሲታወጅ ስትሰማ ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ ደስታ ተገፋፍታ ከጣሪያ በላይ ‹‹…እልልልልል….›› ስትል አዳራሹን አናጋችው..በዙሪያዋ ያሉ ሚዜዎችና አጃቢዎች ተቀላቀሏት…ዘፈኑና ጭፈራው ቀጠለ..፡፡
///
ዘሚካኤል አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ወንበር ከያዘ ደቂቆች አልፈውታል፡፡በአይኑ እየፈለጋት ነው፡፡‹‹በፈጣሪ ስም ወዴት ሄዳሽ ነው?››አጉረመረመ፡፡
ቢፌ የተዘረጋበትን የተንቆጠቆጠ የድግስ አዳራሽ ውብ ሆኖ ይታያል፣ የሰርጉ ድግስ አሁን በደማቅ ሁኔታ እየተካሄደ ነው እና ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ እንግዶች በግዙፉ አዳራሽ ሽር ብትን እያሉ እና እየተዝናኑ ነበር።
‹‹አንድ ባልና ሚስት እንዴት በዚህ መጠን ብዙ ጓደኞች እና ወዳጆች ሊኖራቸው ቻለ?››ሲል አሰበ ፡፡ እና ደግሞ ሁሉም ወደ እሱ ለመቅረብ እና ከእሱ ጋር ውስን ቃላትን ለመለዋወጥም ፈልገው ሲቁነጠነጡ ታዘበ ። እሱ ግን ቀልቡም አይኑም እየተንከራተተ ያለው አንዲትን ሴት ለማየት ነው ።ድንገት ከመድረክ ላይ ከሙሽሮቹ ጀርባ ሆና ተመለከታት፡፡ ግን ወዲያው ተሰወረችበት ፡፡‹‹ዘሚካኤል አረ እራስህን ሰብስብ ››ሲል ራሱን ገሰፀ…ፊቱን ወደግድግዳ አዞረና በእጁ የያዘውን መጠጥ እየተጎነጨ ዘና ለማለት ሞከረ። ቢያንስ እንደዛ በማድረጉ በአይኖቻቸው ሲያሳድዱት የነበሩትን ጎረምሳ ልጃገረዶችን መገላገል ችሏል ፡፡
‹‹ወደዚህ ተንደርድሬ እንድመጣ ያደረገኝ ምንድን ነው?››እራሱን ጠየቀ፡፡ትላንት አመሻሹ ላይ ወደ ዱባይ የመብረር እቅድ ነበረው፡፡ትኬት ሁሉ ቆርጦ ነበር፡፡ከአምስት ቀን በኃላ የሚጀመርና ለተከታታይ ሶስት ቀን የሚካሄድ የሙዚቃ ድግስ አለው፡፡ከአምስት ቀን አስቀድሞ የሚጎዘው…ቀደም ብሎ ከአካባቢው ሁኔታና የአየር ጻባይ ጋር ለመለማመድና ለዝግጅቱ ትኩረት ለመስጠት ስለፈለገ ነበር፡፡እና በፕሮግራሙ መሰረት ሻንጣውና ሸክፎ ወደቦሌ መጓዝ ጀምሮ ነበር..ግን በመንገዱ ላይ የሚያያቸውን ቢል ቦርዶች ሁሉ የልጅቷን ምስል የያዙ እየመሰሉት ሲደነግጥና ፈፅሞ ሊቆጣጠረው የማይችል ስሜት ውስጡ ሲያሸብረው..ወዲያው ስልኩን አውጥቶ ለኤጀንቱ ነበር የደወለው፡፡
‹‹ሄሎ ይቅርታ ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ዛሬ መብረር አልችልም››አለው፡፡
‹‹ምነው..ምን ተፈጠረ?››
‹‹እያመመኝ ነው…አሁን ቦሌ አየር ማረፊያ እየተቃረብኩ ነበር..ግን ወደቤቴ ልመለስ ነው…በረራውን ለሌላ ቀን እንዲሸጋገር አድርግ፡፡››
‹‹ለመቼ ለነገ ላድርገው….?››
‹‹ነገ እንደሚሻለኝ በምን አውቃለው…?ምናልባት ተነገ ወዲያ››
‹‹አውቀሀል …?ዝግጅቱ 5 ቀን እኮ ነው የቀረው››
፡
፡
#ምዕራፍ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹ እንዴት ናችሁ.?.የሴት ወሬ ላይ ነበራችሁ መሰለኝ….በመምጣቴ ምቾት አልተሰማችሁም››አለ፡፡
‹‹እንዴ ባልዬው የሴት ወሬ ደግሞ ምንድነው?››ስትል አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው ወንዷችን ማማት ነዋ››ሲል በፈገግታ መለሰላት፡፡
‹‹አንተ እንደዚህማ አትለንም….በዚህ ፀባይህ ላላገባህ እችላለው…የደገስከው ድግስ ብላሽ እንዳይሆንብህ
ፀአዳ ጣልቃ ገባች‹‹አንቺ እንደዛማ አታስፈራሪውም..እስኪ ልብ ይኑርሽና እምቢ በይው….የልጅ እናቷን ሳይሆን ልጃገረዶችን ነው የማንጋጋለት››ስትል መለሰች፡፡
‹‹አንቺ እስስት ለሁለታችንም እኮ ነው እየተሞገትኩ ያለሁት››
‹‹ያንቺን ሙግት አልፈልግም …ይልቅ ሚካኤል… አንተን እና አዲስአለምን ይቅርታ ልጠይቅህ ፈልጌ ነበር። ››አለችው ኮስተር ብላ፡፡
‹‹ምነው ምን ተፈጠረ?››ሚካኤል ብቻ ሳይሆን አዲስአለምም ያልጠበቀችው ስለነበር ግራ ተጋባች፡፡
‹‹ወንድምህን ዘሚካኤል በሰርጋችሁ ቀን እንዲገኝ ለማድረግ የተቻለኝን ጥሬ ነበር…ግን አልተሳካልኝም፣ አሁን የሚመጣበት ምንም ዕድል የለም።››አለችው፡፡
‹‹ለምን ይቅርታ ትጠይቂያለሽ ? እሱ እንደማይመጣ አስቀድመን እናውቅ ነበር፣››በማለት ሚካኤል ተናገረ፡፡
አሁን ግራ የመጋባቱ ተራ የራሷ የፀዳ ሆነ‹‹ቆይ ለመሞከር እንደሄድኩ ታውቅ ነበር እንዴ?››ስትል በጥርጣሬ ተሞልታ ጠየቀችው፡፡
ፈራ ተባ እያለ በሹክሹክታ‹‹አዎ..አውቅ ነበር››አላት፡፡
ወደአዲስአለም ዞረችና‹‹አንቺ በቃ ሚስጥር የሚባል ነገር አታውቂም..ለዛውም እንዳትነግሪው ብዬ አስጠንቅቄሽ?››
‹‹አንቺ ደግሞ ባልና ሚስት አንድ ሀምሳል አንድ አካል ናቸው ሲባል አልሰማሽም እንዴ? ከገዛ አካሌ ምን ብዬ ነው የምደብቀው?››
‹‹አረ የምትገርሚ ነሽ…ሚኪ ግን በጣም አዝናለው…››
‹‹ምን ያህል እንደሞከርሽና እንደጣርሽ አውቃለው….በእውነት አዲስ በነገረች ቀን እንባ አውጥቼ ነው ያለቀስኩት..ማንም ሰው እዲህ አይነት ነገር ላድርግለህ ብሎኝ አያውቅም ..እህቴ በጣም ነው የምወድሽ …በጣም ነው የማመሰግንሽ››አላት
‹‹እኔም በጣም ነው የምወድህ››አለችና ተንደርድራ ሄዳ ተጠመጠመችበት፡፡እሱም ተቀብሎ አቀፋት፡፡
‹‹እናንተ እኔንም እኮ አስቀናችሁኝ››አለችና ከተቀመጠችበት ሄዳ ሁለቱንም አንድ ላይ አቀፈቻቸው፡፡
///
መድረስ አይቀርም ለአመታት ሲታሰብበት እና ለወራት ሲለፋበት የነበር የሰርግ ቀን ደርሶ አዳራሽ ሙሉ እድምተኞች ሙሽሮቹን አጅቦ ሽር ብትን እያሉ ነው፡፡ ፀአዳ በህይወቷ ከዚህ በፊት እንደዚህ አይነት ደስታና ፈንጠዝያ ተሰምቷት አያውቅም?ከሙሽራዋ ጀርባ ሆና በደመቀ ሁኔታ የሚካሄደውን ስነስርዓት እየተከታተለች ነው፡፡በአዲስ አለም የሰርግ ቀሚስ ላይ ያለው የተራቀቀ ዶቃ በመስታወት ላይ ሲያርፍ በተብረቀረቀ ብርሃን አንጸባርቆ መልሶ ወደውስጥ ሲረጭ ስትመለከት በተረት አለም ውስጥ ስላሉ ልዕልቶች እንድታስብ አደረጋት። የአጋቢውን ፓስተር ድምጽ ላይ ለማተኮር ሞክራለች። እሷ ራሷ የለበሰችው ቀሚስ ልዩ አይነት ስሜት እንዲሰማት አድርጓታል…በህይወቷ መቼ ቀሚስ ለብሳ እንደነበረ አታስታውስም፡፡ ምን አልባት ከቤተሰቦቾ ጠፍታ ከወጣች በኃላ ቀሚስ ጨርሱኑ ለብሳ አታውቅም ይሆናል…ሴት መሆኗ እንዲሰማት አትፈልግም…ጠንካራ ታጋይ ሆና ልጇን ማሳደግና ህይወትና ማሸነፍ ብቻ ነው እቅዷ ..ቀሚስ መልበስ ለስላሳ የሚያደርጋት ይመስላታል…በምን ምክንያት እንደዛ ልታስብ እንደቻለች አታውቅም..ግን ደግሞ ትክክል ነበረች፡፡ ይሄው ዛሬ የተለየ ስሜት እየተሰማት ነው…ሴትነቷ ጎልቶ እየበራ ነው…ይሄ ደግሟ ለሚመለከቷት ሰዎች ብቻ ሳይሆን… ለራሷም በደንብ ታውቋታል፡፡ አዲስአለም የሚካኤልን እጅ በመያዝ አጋቢው ፓስተሩ የሚላትን ጥምረታቸውን የሚያበስሩ ውብ ቃላትን ጥርት ባለ ድምፅ ስትደግም ይሰማል… ።
በመከራህም ሆነ በደስታ ጊዜ… ላልለይህ ቃል እገባለው፡፡
በሀዘንህም ሆነ በደስታህ …ጊዜ ከጎንህ ልሆን ቃል እገባለው፡፡
በጤንነትህም ሆነ በህመምህ ጊዜ …ከጎንህ ላልለይ ቃል እገባልው፡፡
ቀላበቱን አውጥቶ አጠለቀላት እሷም አጠለቀችለት፡፡እርስ በርስ እንዲሳሳሙ ተደረገ….ፀደይ በምታየው ነገር ሁሉ አንሳፋፊ አይነት አስካሪ ስሜት እየተሰማት ነው፡፡
እሷ ከረጅም ጊዜ በፊት ነው በደስታ ማመን ያቆመችው፣ ነገር ግን እዚህ ውብ ቦታ ላይ ሆና አዲስአለም እና ሚካኤል ከዚህች ደቂቃ ጀምሮ ባልና ሚስት መሆናቸውን በፓስተሩ ሲታወጅ ስትሰማ ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ ደስታ ተገፋፍታ ከጣሪያ በላይ ‹‹…እልልልልል….›› ስትል አዳራሹን አናጋችው..በዙሪያዋ ያሉ ሚዜዎችና አጃቢዎች ተቀላቀሏት…ዘፈኑና ጭፈራው ቀጠለ..፡፡
///
ዘሚካኤል አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ወንበር ከያዘ ደቂቆች አልፈውታል፡፡በአይኑ እየፈለጋት ነው፡፡‹‹በፈጣሪ ስም ወዴት ሄዳሽ ነው?››አጉረመረመ፡፡
ቢፌ የተዘረጋበትን የተንቆጠቆጠ የድግስ አዳራሽ ውብ ሆኖ ይታያል፣ የሰርጉ ድግስ አሁን በደማቅ ሁኔታ እየተካሄደ ነው እና ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ እንግዶች በግዙፉ አዳራሽ ሽር ብትን እያሉ እና እየተዝናኑ ነበር።
‹‹አንድ ባልና ሚስት እንዴት በዚህ መጠን ብዙ ጓደኞች እና ወዳጆች ሊኖራቸው ቻለ?››ሲል አሰበ ፡፡ እና ደግሞ ሁሉም ወደ እሱ ለመቅረብ እና ከእሱ ጋር ውስን ቃላትን ለመለዋወጥም ፈልገው ሲቁነጠነጡ ታዘበ ። እሱ ግን ቀልቡም አይኑም እየተንከራተተ ያለው አንዲትን ሴት ለማየት ነው ።ድንገት ከመድረክ ላይ ከሙሽሮቹ ጀርባ ሆና ተመለከታት፡፡ ግን ወዲያው ተሰወረችበት ፡፡‹‹ዘሚካኤል አረ እራስህን ሰብስብ ››ሲል ራሱን ገሰፀ…ፊቱን ወደግድግዳ አዞረና በእጁ የያዘውን መጠጥ እየተጎነጨ ዘና ለማለት ሞከረ። ቢያንስ እንደዛ በማድረጉ በአይኖቻቸው ሲያሳድዱት የነበሩትን ጎረምሳ ልጃገረዶችን መገላገል ችሏል ፡፡
‹‹ወደዚህ ተንደርድሬ እንድመጣ ያደረገኝ ምንድን ነው?››እራሱን ጠየቀ፡፡ትላንት አመሻሹ ላይ ወደ ዱባይ የመብረር እቅድ ነበረው፡፡ትኬት ሁሉ ቆርጦ ነበር፡፡ከአምስት ቀን በኃላ የሚጀመርና ለተከታታይ ሶስት ቀን የሚካሄድ የሙዚቃ ድግስ አለው፡፡ከአምስት ቀን አስቀድሞ የሚጎዘው…ቀደም ብሎ ከአካባቢው ሁኔታና የአየር ጻባይ ጋር ለመለማመድና ለዝግጅቱ ትኩረት ለመስጠት ስለፈለገ ነበር፡፡እና በፕሮግራሙ መሰረት ሻንጣውና ሸክፎ ወደቦሌ መጓዝ ጀምሮ ነበር..ግን በመንገዱ ላይ የሚያያቸውን ቢል ቦርዶች ሁሉ የልጅቷን ምስል የያዙ እየመሰሉት ሲደነግጥና ፈፅሞ ሊቆጣጠረው የማይችል ስሜት ውስጡ ሲያሸብረው..ወዲያው ስልኩን አውጥቶ ለኤጀንቱ ነበር የደወለው፡፡
‹‹ሄሎ ይቅርታ ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ዛሬ መብረር አልችልም››አለው፡፡
‹‹ምነው..ምን ተፈጠረ?››
‹‹እያመመኝ ነው…አሁን ቦሌ አየር ማረፊያ እየተቃረብኩ ነበር..ግን ወደቤቴ ልመለስ ነው…በረራውን ለሌላ ቀን እንዲሸጋገር አድርግ፡፡››
‹‹ለመቼ ለነገ ላድርገው….?››
‹‹ነገ እንደሚሻለኝ በምን አውቃለው…?ምናልባት ተነገ ወዲያ››
‹‹አውቀሀል …?ዝግጅቱ 5 ቀን እኮ ነው የቀረው››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዘሚካኤል ከሰዓታት በፊት የሰርጉን ስፍራ ለቆ መሄድ ነበረበት። ነገር ግን ከፀአዳ ተለይቶ መራመድ አልቻለም። ከሳምንት በፊት በእንጥልጥል የተወውን ጉዳይ መቋጫ ማበጀት አለበት፡፡በልቡ ጭራበት የሄደችው ሲኦል እሳት እየተንበለበለች መላ ሰውነቱ ትኩሳት እንደለቀቀችበት ነው…እንዴትም አድርጎ እንዴት እሱን ማስተካከል ያስፈልገዋል. ዛሬ ማታ።
ፀአዳ ለዘሚካኤል ቃል በገባችለት መሰረት ወደእሱ ለመሄድ ከውስጥ ወደአዳራሹ በተመለሰች ጊዜ በብዙ ውብና አማላይ ሴቶች ተከቦ ሲያውካካ ተመለከተችውና ከመንገዱ ለመራቅ ወሰነች - ባየችው ነገር ክፍት ነው ያላት…እንደዛ የማድረግ መብት የላትም ..ግን ከማንም ለመፎካከርና እሱን ሻሞ ለመሻማት ምንም አይነት እቅድ የላትም..እና እግሯና ወደኃላ ጎተተችና የአስተባባሪነቱን ስራዋን በትኩረት መስራቷን ጀመረች፡፡እራሷን ማሞኘት አልፈለገችም።
እሱ በእጁ ይዞ የነበረውን ባዶ ብርጭቆ በአጠገቡ በሚያልፈው አስተናጋጅ ትሪ ላይ አስቀመጠና ዓይኑን ወደ ህዝቡ መሀከል አንከራተተ። የሙሽሮቹ ዋና ተጠሪ እንደመሆኗ መጠን መጥፋት አልቻለችም። ግን እሱን ከእይታዋ ለማስወገድ እየሞከረች እንደሆነ ያስታውቅባታል፡፡‹‹እንደዛ እንድታደርጊማ አልፈቅድልሽም››ሲል ፎከረ፡፡ይሄ በእሱ ልምድ አዲስ ተሞክሮ ነበር።አንድ በሆነ አጋጣሚ ከንፈሩን የቀመሰች ሴት መልሳ ልታገኘው መከራዋን ስታይና ስትንሰፈሰፍ ነበር የሚያውቀው፣ከከበቡት ልጃገረዶች በዘዴ ተለየና እሷን ለማግኘት መጣር ጀመረ፡፡
ፀደይ ግራ በመጋባት ያለአላማ ከወዲህ ወዲያ ስትሽከረከር . ድንገት አይን አዲስ ወደእሷ ጠራቻት‹‹እ ምን ፈለግሽ?››
‹‹እኔ ምንም አልፈለኩም… ለምን ከእሱ ትደበቂያለሽ ?››
‹‹ አልተደበቅኩም›› አለች ፀአዳ፡፡
‹‹እሺ እንደዚያ ከሆነ፣ ለምንድነው ከእሱ ጎን ሆነሽ አንድ ብርጭቆ ሻምፓኝ የማትጎነጪው?ምንድነው የሚያስፈራሽ?››
‹‹እንደምታይው እሱ ብቸኛ ሰው አይደለም….ሁሉም ሰው የእሱን እዚህ ሰርግ ላይ ስለመገኘት ነው የሚያወራው -..እና ወደሰርግ አዳራሹ ከገባበት ደቂቃ አንስቶ በሰው በተለይ በሴቶች እንደተከበበ ነው››
‹‹እና ውድድሩን አላሸንፍም ብለሽ ሰጋሽ …?አዎ ከባድ ውድድር እንዳለብሽ እኔም ገምታለው።ግን እኮ ይሄንን ለመሰለ ጠንበልል አማቼ… መፋለም መቻል በራሱ እድል ነው?››
‹‹አረ በካሽ…እኔ ፀደይ ነኝ፡፡ ወንድ ለማግኘት ከሌላ ሴት ጋር የምናጠቀው። እንደው እንዳልሺው ፊልሚያ ውስጥ ልግባ ብልስ እሱ ፍላጎት ከሌለው የሚሆን ይመስልሻል…?እናስ ከእነዛ ከከተመዋ አማላይና ስብር ቅንጥስ ከሚሉ ወዳጆችሽ ጎልቼ በአይኑ የምገባ ይመስልሻል...›› በብስጭት ተንዘረዘረች፡፡
‹‹ገባሽ እኮ ..ቀድመሽ በከንፈሩ ገባሽ….ይልቅ አትንቀርፋፊ..በሰርጌ ቀን ካንቺ ጋር ከዚህ በላይ መዳረቅ አልችልም..ባሌ አየጠራኝ ነው፡፡ቻው››ብላት በቆመችበት ጥላት ሄደች፡፡
ፀደይ ለተወሰነ ደቂቃ ድንዘዝዝ አለች‹‹…ምን ላድርግ?››እራሷን ጠየቀች..፡፡ምንም ያህል ችላ ልትለውና ልትርቀው ብትሞክርም ልቧ ግን ልክ እንደማግኔት ወደእሱ እየጎተታት ነው…ወደአለበት ሄዳ ከሰውዬው ጋር ለመነጋገር ድፍረት አልነበራትም።ፊቷን አዙራም ከእሱ ርቃ ለመሰወር ብትጥርም ከዚህ የበለጠ ተጫማሪ ሳዕታትን ከእሱ ተደብቃ መቆየት እንደማትችል ልቧ ያውቃል፡፡ድንገት ስታየው ብቻውን ሆኖ ስላየችው ወደኋላ ተመለሰችና ቅዱስን ከሞግዚቷ ተቀብላ በማቀፍ እንደምንም እራሷን አደፋፍራ ወደእሱ ሄደች፡፡
‹‹እንዴት ነሽ…?መምጣትሽን በናፍቆት ስጠብቅ ነበር››ከአንደበቷ የሚወጡት ቃላት ልቧን በቀላሉ ማቅለጥ አቅም ነበራቸው፡፡
‹‹አልደበረህም አይደል?››
‹‹በመጠኑ…ግን በጣም የሚፈልጉትን ነገር ባልተመቸ ሁኔታ ውስጥም ሆነው መጠበቅ የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው….እና አልከፋኝም››አላት፡፡
ዝም አለች…ምን እንደምትል ግራ ተገባች‹‹ከወንድምህ ልጅ ከቅዱስ ጋር ላስተዋውቅህ።››አለችው
ዘሚካኤል በተራው በዝምታ ተዋጠና ህፃኑን በትኩረት ማየቱን ቀጠለ። የሆነ የማያውቀው መከፋት ስሜት ውስጡን ሲያተረማምሰው ተሰማው፡፡ህፃኑን እቅፉ የተንጠለጠሉትን ውብ ጉንጮቹን እያገላበጠ ቢሰመው ደስ ይለው ነበር፤አዎ እንደዛ አይነት ፍላጎት ነበር የተሰማው፡፡ግን ከተቀመጠበት መነቃነቅ ሆነ እጆቹን ማንቀሳቀስ አልቻለም፡፡እንዲህ መሆን የለበትም ነበር፡፡እሱ በቤተሰቡ ላይ ያን አይነት መአት ከመድረሱ በፊት በጣም ሰው ወዳጅ በተለይ ዘመድ ለተባለ ሰው ልቡ ትርክክ የሚል በፍቅር የሞላ ልጅ ነበር፡፡ከክስተቱ በኋላ ግን ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ነው የሆነው፡፡ከዘመድ ጋር መነካካት መርዝ እንደመጎንጨት የሚያንገፈግፈው ነገር ሆኖል…ቢሆንም እንዲህ በጮርቃ ህፃን ላይ እንኳን የተለየ አቋም ሊኖረው አይገባም ነበር፡፡
‹‹አይዞህ አትጨናነቅ..በሂደት ጥሩ አጎቱ ትሆናለህ››አለችው፡፡
‹‹ልጁን በተመለከተ እንደጨነቀኝ እንዴት አወቀች?››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡
‹‹አሁንም ብቻህን ጥዬህ ልሄድ ነው..ግን አልቆይም..ህፃኑን ለእናቱ አስረክቤ መጣሁ…››
በረጅሙ ተነፈሰ‹‹አዎ እንደዛ ይሻላል..አታስቢ ስለአንቺ እያሰብኩ ጠብቅሻለሁ፡፡››አላት፡፡
ፈገግ አለችለትና ህፃኑን ቅዱስን አቅፋ ተነስታ ሄደች፡፡ከኃላ አይኑን ተክሎ ተመለከታት..አቋሞ ልዩ ነው፡፡ተረከዘ ሎሚ የምትባል አይነት ነች..እንዲህ አይነት እግር ያላት ሴት ከድሮውም በጣም ነው የምትማርከው…ደግሞ ከሁሉም በላይ እሱ ጋር ከሚመላለሱት ሴቶች ተቃራኒ በሆነ መልኩ ምንም አይነት መዋቢያና መኳኳያ አትጠቀምም…ለምን እንደሆነ ሊገባው አልቻለም…ብትጠቀም እኮ የበለጠ ውብ ትሆን ነበር?››ሲል አሰበ፡፡‹‹ግን አንኳንም አልተጠቀመች››ሲል ደመደመ፡፡
ልጁን ለሞግዚቷ አስረክባ ብቻዋን ትመጣለች ብሎ ሲጠብቅ የወንድሙን ሚስት አስከትላ መጣች፡፡
አዲስአለም ‹‹ዘሚካኤል… በመምጣትህ በጣም ደስ ብሎናል … ዛሬ ማታ ቤታችን በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ ብትገኝ እንዴት ደስ ይለናል መሰለህ …ግን ምቾት የማይሰማህ ከሆነ እንረዳሀለን….እዚህ ስለመጣህ እራሱ በእውነት በጣም ደስተኛ አድርገሀናል….ሰርጋችንም የማይረሳና የታደመው ሰው ሁሉ መቼም የሚያስታወስው እንዲሆን አድርገሀል ።››
ዘሚካኤል ደቂቃ ወስዶ እንደማሰብ ሲያደርግ ፀአዳ ጣልቃ ገብታ‹‹እባክህ እሺ ብለህ ቆይ…አይዞህ እንደአሁኑ ጣል ጣል አናደርግህም…ቃል እገባልሀለው››አለችው፡፡
ንግግሯን ስታጠናቅቅ አዲስአለምም ሆነች ዘሚካኤል አፍጥጠው እየተመለከቷት ነበር…‹‹ምንድነው የሚያስቀበጥረኝ ?››ስትል በውስጧ እራሷን ወቀሰች፡፡
ዘሚካኤል መናገር ጀመረ‹‹እሺ እቆያለው››ሲል ተናገረ፡፡
አዲስአለም ፊት በደስታ በራ‹‹አመሰግናለው..በቃ አሁን ጥያችሁ ልሂድ …አብረሽው ቆይና ይዘሽውን ነይ››አለችና ተመልሳ ሄደች፡፡
ፀአዳ ከእፍረቷ ሳትላቀቅ በዝግታ ተቀመጠችና፡፡‹‹እሺ ትላለህ ብዬ አላሰብኩም ነበር››አለችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር እኔም እሺ እላለው የሚል ግምት አልነበረኝም….ቃልሽን አምኜ ነው እሺ ያልኩት››አላት፡፡
‹‹ማለት የምን ቃል?››
‹‹እንደእስካሁኑ ብቻህን በመተው እንድትደበር አላደርግህም…ከመጀመሪያው እስከፍጻሜው ከጎንህ አልለይም…›ብለሽ የገባሽልኝን ቃል ነዋ››
‹‹አንተ ይሄን ሁሉ መቼ ነው የተናገርኩት.››
‹‹.አሁን ከደቂቃዎች በፊት››
‹‹ይሁን..ለማንኛውም ማትቆጭበት ውሳኔ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለው››
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዘሚካኤል ከሰዓታት በፊት የሰርጉን ስፍራ ለቆ መሄድ ነበረበት። ነገር ግን ከፀአዳ ተለይቶ መራመድ አልቻለም። ከሳምንት በፊት በእንጥልጥል የተወውን ጉዳይ መቋጫ ማበጀት አለበት፡፡በልቡ ጭራበት የሄደችው ሲኦል እሳት እየተንበለበለች መላ ሰውነቱ ትኩሳት እንደለቀቀችበት ነው…እንዴትም አድርጎ እንዴት እሱን ማስተካከል ያስፈልገዋል. ዛሬ ማታ።
ፀአዳ ለዘሚካኤል ቃል በገባችለት መሰረት ወደእሱ ለመሄድ ከውስጥ ወደአዳራሹ በተመለሰች ጊዜ በብዙ ውብና አማላይ ሴቶች ተከቦ ሲያውካካ ተመለከተችውና ከመንገዱ ለመራቅ ወሰነች - ባየችው ነገር ክፍት ነው ያላት…እንደዛ የማድረግ መብት የላትም ..ግን ከማንም ለመፎካከርና እሱን ሻሞ ለመሻማት ምንም አይነት እቅድ የላትም..እና እግሯና ወደኃላ ጎተተችና የአስተባባሪነቱን ስራዋን በትኩረት መስራቷን ጀመረች፡፡እራሷን ማሞኘት አልፈለገችም።
እሱ በእጁ ይዞ የነበረውን ባዶ ብርጭቆ በአጠገቡ በሚያልፈው አስተናጋጅ ትሪ ላይ አስቀመጠና ዓይኑን ወደ ህዝቡ መሀከል አንከራተተ። የሙሽሮቹ ዋና ተጠሪ እንደመሆኗ መጠን መጥፋት አልቻለችም። ግን እሱን ከእይታዋ ለማስወገድ እየሞከረች እንደሆነ ያስታውቅባታል፡፡‹‹እንደዛ እንድታደርጊማ አልፈቅድልሽም››ሲል ፎከረ፡፡ይሄ በእሱ ልምድ አዲስ ተሞክሮ ነበር።አንድ በሆነ አጋጣሚ ከንፈሩን የቀመሰች ሴት መልሳ ልታገኘው መከራዋን ስታይና ስትንሰፈሰፍ ነበር የሚያውቀው፣ከከበቡት ልጃገረዶች በዘዴ ተለየና እሷን ለማግኘት መጣር ጀመረ፡፡
ፀደይ ግራ በመጋባት ያለአላማ ከወዲህ ወዲያ ስትሽከረከር . ድንገት አይን አዲስ ወደእሷ ጠራቻት‹‹እ ምን ፈለግሽ?››
‹‹እኔ ምንም አልፈለኩም… ለምን ከእሱ ትደበቂያለሽ ?››
‹‹ አልተደበቅኩም›› አለች ፀአዳ፡፡
‹‹እሺ እንደዚያ ከሆነ፣ ለምንድነው ከእሱ ጎን ሆነሽ አንድ ብርጭቆ ሻምፓኝ የማትጎነጪው?ምንድነው የሚያስፈራሽ?››
‹‹እንደምታይው እሱ ብቸኛ ሰው አይደለም….ሁሉም ሰው የእሱን እዚህ ሰርግ ላይ ስለመገኘት ነው የሚያወራው -..እና ወደሰርግ አዳራሹ ከገባበት ደቂቃ አንስቶ በሰው በተለይ በሴቶች እንደተከበበ ነው››
‹‹እና ውድድሩን አላሸንፍም ብለሽ ሰጋሽ …?አዎ ከባድ ውድድር እንዳለብሽ እኔም ገምታለው።ግን እኮ ይሄንን ለመሰለ ጠንበልል አማቼ… መፋለም መቻል በራሱ እድል ነው?››
‹‹አረ በካሽ…እኔ ፀደይ ነኝ፡፡ ወንድ ለማግኘት ከሌላ ሴት ጋር የምናጠቀው። እንደው እንዳልሺው ፊልሚያ ውስጥ ልግባ ብልስ እሱ ፍላጎት ከሌለው የሚሆን ይመስልሻል…?እናስ ከእነዛ ከከተመዋ አማላይና ስብር ቅንጥስ ከሚሉ ወዳጆችሽ ጎልቼ በአይኑ የምገባ ይመስልሻል...›› በብስጭት ተንዘረዘረች፡፡
‹‹ገባሽ እኮ ..ቀድመሽ በከንፈሩ ገባሽ….ይልቅ አትንቀርፋፊ..በሰርጌ ቀን ካንቺ ጋር ከዚህ በላይ መዳረቅ አልችልም..ባሌ አየጠራኝ ነው፡፡ቻው››ብላት በቆመችበት ጥላት ሄደች፡፡
ፀደይ ለተወሰነ ደቂቃ ድንዘዝዝ አለች‹‹…ምን ላድርግ?››እራሷን ጠየቀች..፡፡ምንም ያህል ችላ ልትለውና ልትርቀው ብትሞክርም ልቧ ግን ልክ እንደማግኔት ወደእሱ እየጎተታት ነው…ወደአለበት ሄዳ ከሰውዬው ጋር ለመነጋገር ድፍረት አልነበራትም።ፊቷን አዙራም ከእሱ ርቃ ለመሰወር ብትጥርም ከዚህ የበለጠ ተጫማሪ ሳዕታትን ከእሱ ተደብቃ መቆየት እንደማትችል ልቧ ያውቃል፡፡ድንገት ስታየው ብቻውን ሆኖ ስላየችው ወደኋላ ተመለሰችና ቅዱስን ከሞግዚቷ ተቀብላ በማቀፍ እንደምንም እራሷን አደፋፍራ ወደእሱ ሄደች፡፡
‹‹እንዴት ነሽ…?መምጣትሽን በናፍቆት ስጠብቅ ነበር››ከአንደበቷ የሚወጡት ቃላት ልቧን በቀላሉ ማቅለጥ አቅም ነበራቸው፡፡
‹‹አልደበረህም አይደል?››
‹‹በመጠኑ…ግን በጣም የሚፈልጉትን ነገር ባልተመቸ ሁኔታ ውስጥም ሆነው መጠበቅ የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው….እና አልከፋኝም››አላት፡፡
ዝም አለች…ምን እንደምትል ግራ ተገባች‹‹ከወንድምህ ልጅ ከቅዱስ ጋር ላስተዋውቅህ።››አለችው
ዘሚካኤል በተራው በዝምታ ተዋጠና ህፃኑን በትኩረት ማየቱን ቀጠለ። የሆነ የማያውቀው መከፋት ስሜት ውስጡን ሲያተረማምሰው ተሰማው፡፡ህፃኑን እቅፉ የተንጠለጠሉትን ውብ ጉንጮቹን እያገላበጠ ቢሰመው ደስ ይለው ነበር፤አዎ እንደዛ አይነት ፍላጎት ነበር የተሰማው፡፡ግን ከተቀመጠበት መነቃነቅ ሆነ እጆቹን ማንቀሳቀስ አልቻለም፡፡እንዲህ መሆን የለበትም ነበር፡፡እሱ በቤተሰቡ ላይ ያን አይነት መአት ከመድረሱ በፊት በጣም ሰው ወዳጅ በተለይ ዘመድ ለተባለ ሰው ልቡ ትርክክ የሚል በፍቅር የሞላ ልጅ ነበር፡፡ከክስተቱ በኋላ ግን ሙሉ በሙሉ ሌላ ሰው ነው የሆነው፡፡ከዘመድ ጋር መነካካት መርዝ እንደመጎንጨት የሚያንገፈግፈው ነገር ሆኖል…ቢሆንም እንዲህ በጮርቃ ህፃን ላይ እንኳን የተለየ አቋም ሊኖረው አይገባም ነበር፡፡
‹‹አይዞህ አትጨናነቅ..በሂደት ጥሩ አጎቱ ትሆናለህ››አለችው፡፡
‹‹ልጁን በተመለከተ እንደጨነቀኝ እንዴት አወቀች?››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡
‹‹አሁንም ብቻህን ጥዬህ ልሄድ ነው..ግን አልቆይም..ህፃኑን ለእናቱ አስረክቤ መጣሁ…››
በረጅሙ ተነፈሰ‹‹አዎ እንደዛ ይሻላል..አታስቢ ስለአንቺ እያሰብኩ ጠብቅሻለሁ፡፡››አላት፡፡
ፈገግ አለችለትና ህፃኑን ቅዱስን አቅፋ ተነስታ ሄደች፡፡ከኃላ አይኑን ተክሎ ተመለከታት..አቋሞ ልዩ ነው፡፡ተረከዘ ሎሚ የምትባል አይነት ነች..እንዲህ አይነት እግር ያላት ሴት ከድሮውም በጣም ነው የምትማርከው…ደግሞ ከሁሉም በላይ እሱ ጋር ከሚመላለሱት ሴቶች ተቃራኒ በሆነ መልኩ ምንም አይነት መዋቢያና መኳኳያ አትጠቀምም…ለምን እንደሆነ ሊገባው አልቻለም…ብትጠቀም እኮ የበለጠ ውብ ትሆን ነበር?››ሲል አሰበ፡፡‹‹ግን አንኳንም አልተጠቀመች››ሲል ደመደመ፡፡
ልጁን ለሞግዚቷ አስረክባ ብቻዋን ትመጣለች ብሎ ሲጠብቅ የወንድሙን ሚስት አስከትላ መጣች፡፡
አዲስአለም ‹‹ዘሚካኤል… በመምጣትህ በጣም ደስ ብሎናል … ዛሬ ማታ ቤታችን በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ ብትገኝ እንዴት ደስ ይለናል መሰለህ …ግን ምቾት የማይሰማህ ከሆነ እንረዳሀለን….እዚህ ስለመጣህ እራሱ በእውነት በጣም ደስተኛ አድርገሀናል….ሰርጋችንም የማይረሳና የታደመው ሰው ሁሉ መቼም የሚያስታወስው እንዲሆን አድርገሀል ።››
ዘሚካኤል ደቂቃ ወስዶ እንደማሰብ ሲያደርግ ፀአዳ ጣልቃ ገብታ‹‹እባክህ እሺ ብለህ ቆይ…አይዞህ እንደአሁኑ ጣል ጣል አናደርግህም…ቃል እገባልሀለው››አለችው፡፡
ንግግሯን ስታጠናቅቅ አዲስአለምም ሆነች ዘሚካኤል አፍጥጠው እየተመለከቷት ነበር…‹‹ምንድነው የሚያስቀበጥረኝ ?››ስትል በውስጧ እራሷን ወቀሰች፡፡
ዘሚካኤል መናገር ጀመረ‹‹እሺ እቆያለው››ሲል ተናገረ፡፡
አዲስአለም ፊት በደስታ በራ‹‹አመሰግናለው..በቃ አሁን ጥያችሁ ልሂድ …አብረሽው ቆይና ይዘሽውን ነይ››አለችና ተመልሳ ሄደች፡፡
ፀአዳ ከእፍረቷ ሳትላቀቅ በዝግታ ተቀመጠችና፡፡‹‹እሺ ትላለህ ብዬ አላሰብኩም ነበር››አለችው፡፡
‹‹እውነቱን ለመናገር እኔም እሺ እላለው የሚል ግምት አልነበረኝም….ቃልሽን አምኜ ነው እሺ ያልኩት››አላት፡፡
‹‹ማለት የምን ቃል?››
‹‹እንደእስካሁኑ ብቻህን በመተው እንድትደበር አላደርግህም…ከመጀመሪያው እስከፍጻሜው ከጎንህ አልለይም…›ብለሽ የገባሽልኝን ቃል ነዋ››
‹‹አንተ ይሄን ሁሉ መቼ ነው የተናገርኩት.››
‹‹.አሁን ከደቂቃዎች በፊት››
‹‹ይሁን..ለማንኛውም ማትቆጭበት ውሳኔ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለው››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡
‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት
‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››
‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡
አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ
‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡
‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››
‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››
‹‹ድንግልናሽን?››
‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››
‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…
‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡
‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››
‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››
‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››
‹‹ማለት?››
‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡
‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››
‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡
‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡
‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››
‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››
‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››
‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››
‹‹ምን ያስፈራሀል?››
‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››
‹‹እንዴት …?››
‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››
‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››
‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››
‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››
‹‹ማለት?፡፡››
‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡
‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡
‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡
‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡
‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››
‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››
‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡
‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡
አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››
ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡
በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡ ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡
በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ከሰርግ ግርግሩ በኋላ አዲስ አለምና ሚካኤል ወደመኝታ ቤታቸው ገብተው ልጃቸውን መሀል አድርገው ተኝተዋል፡፡
‹‹አረ እስኪ ዛሬ እንኳን ከመሀል አስወጪው››አላት
‹‹ምነው በልጅህ መቅናት ጀመርክ እንዴ?››
‹‹አዎ …አይገርምሽም ለካ ወንድ ልጅ ለአባቱ የመጀመሪያው ጣውንት ነው..አሁን አይደል ያወቅኩት….በይ አሁን ከመሀል አውጪው››አለ እየሳቀ፡፡
አዲስ አለም ቅዱስን ከመሀከል በማውጣት ከእሷ ጎን አስተኛችውና ‹‹እንዲህ አይነት ነጭናጫ መሆንህን ባውቅ ኖሮ መቼም አላገባህም ነበር›› አለችው።ሚካኤል ነፃ እጁን በዳሌዋ ላይ አሳርፎ ወደ እቅፍ ጎተታት። ጥንካሬውን ተቋቁማ ከእቅፉ ለማምለጥ ታገለቸው….በቀላሉ ልታሸንፈው አልቻለችም፡፡ ከተኛበት ተነሳና ጭና መሀከል ገባ…
ያልተጠበቀ አስደሳች የፍቅር ጊዜ አሳለፉና ሁለቱም ደክሟቸው በየፊናቸው ተዘረሩ ..ከተወሰነ እርፍትና መረጋጋት በኃላ
‹‹ያለፍቃዴ እንደደፈርከኝ ቁጠረው…ለእኔ መልአክ ለመሆን፣ ልትወደኝና፣ ልታከብረኝ ከዛም አልፎ ልትታዘዘኝ ቃል ገብተሀል …ይህንን በአንድ ቀን ልትረሳው አትችልም፡፡ምነው ረሳሀው እንዴ ?››አለችው፡፡
‹‹አንቺም እኮ እንደሙሽርነትሽ የሚጠበቅብሽን ነገር አላገኙሁብሽም››
‹‹አንተ ..ደግሞ ምንድነው ፈልገህ ያጣህብኝ?››
‹‹ድንግልናሽን?››
‹‹አንተ የተረገምክ …እሱንማ ተስገብግበህ ከ5 ኣመት በፊት ቀርጥፈህ በላኸው …አሁን ከየት ላምጣልህ…የፋብሪካ ውጤት አይደል አላሳበይደው?››
‹‹እንዴ …የእውነትሽን ነው…?ዘንግቼው እኮ ነው…..እኔው ነበርኩ የወሰድኩት?››አላት እየሳቀ…
‹‹አንተ ገና ይሄንን ልጅ እኔ ነኝ የወለድኩት?ማለትህ አይቀርም…››ሳቀች፡፡
‹‹አይ እሱን እንኳን አልልም..በልጄ ቀልድ የለም?››
‹‹እና በሚስት ነው ቀልድ ያለው››
‹‹በሚስት ሳይሆን በድንግልና….አንቺ ቀልዱ ቀልድ ነው…..ፀዲ ግን እንዴት ነው?››
‹‹ማለት?››
‹‹ማታ ከዘሚካኤል ጋር ተያይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም….ሰርጉ ላይ ሁሉ ስትንሾካሾኩ ነበር..ምን እየተካሄደ ነው?››የቆረቆረውን ነገር ጠየቃት፡፡
‹‹ለእኔም ጓደኛዬ እንደሆነች ሁሉ ለአንተም ጓደኛህ ነች…ደውለህ ጠይቃት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም››
‹‹አንተ…ተአምር ተፈጥሮ ከአመታት በኃላ ከወንድ ጋር ተያይዛ ብትወጣ ልትረብሻት ትደውልላታለህ?፡፡››አለችው በመገረም፡፡
‹‹መደወል አልነበረብኝም እንዴ?››አለ ደንግጦ፡፡
‹‹አልነበረብህም..ለማንኛውም ወንድምህ ቀልቡን ጥሎባታል››
‹‹እንዴት እንዴት ሆኖ…?.ማለት ትናንት ሰርግ ላይ ሲገናኙ ሁለተኛ ቀናቸው አይደል….?.››
‹‹አንዳንድ ፍቅር እንደዛ ነው…..››
‹‹ፍቅር አለሺው…ብቻ እወነቱን ንገረኝ ካልሽ በጣም ፈርቼለው››
‹‹ምን ያስፈራሀል?››
‹‹ፀዲ በመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ምን ያህል እንደተጎዳችና ስንት መከራ እንዳሳለፈች በደንብ ታውቂያለሽ..ዳግመኛ ተመሳሳይ አይነት ስቃይ ላለማሳለፍ ለአመታት ከወንድ እርቃ ነው የኖረችው….እና አሁን እንዳልሺው ከዘሚካኤል ጋር የተጀመረ ነገር ካለ መጨረሻው ጥሩ እንደማይሆን እኔም አንቺም እናውቃለን፡፡››
‹‹እንዴት …?››
‹‹ምን እንዴት አለው…?የዘሚካኤልን ፀባይ የምታውቂው ነው››
‹‹ተው እንጂ ከወንድምህ ከተለያየህ እኮ 7 አመት አልፏሀል…በዚህ ሁሉ አመት ውስጥ ምን አይነት ሰው እንደሆነ ልትገምት አትችልም፡፡››
‹‹ለረጅም ጊዜ አብሬው ባልኖርም…በየሚዲያውና በየጋዜጣው ስለእሱ የሚባልውናና የሚፃፈውን ተከታትዬ እንደማነብ ታውቂያለሽ….ከአንድ ሴት ጋር አንድ ወር እንኳን ቆየ ሲባል ሰምቼ አላውቅም፡፡››
‹‹አይዞህ አትፍራ…እንደሰጋሀው ከእሱ ጋር እንኳን ዘላቂ ግንኙነት ባይኖራትም የተዳፈነውን እና ያረጀውን ስሜቷን ቢያነቃቃላት ቀላል ነገር አይደለም፡፡››
‹‹ማለት?፡፡››
‹‹ምን መሰለህ…ፀዲ የመጀመሪያ ፍቅረኛዋ ጋር ፍቅር የሰራችው መቼ ነው… በ17 አመቷ….በዛ ጊዜ እሷም ሆነች ፍቅረኛዋ በጣም ልጆች ከመሆናቸው በተጨማሪ ልምድ አልባዎች ነበሩ…ምን አልባት በየዋህነት ተቃቅፈው ሲተሸሹ ነው በድንገት ግንኙነት የፈፀሙትና እሷ ያረገዘችው፡፡እንደነገረችኝ ከሆነ ያ የሆነው ለአንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ያ ማለት ስለመሳሳም….ስለወሲብ …ጣዕም ምንም የምታስታውሰውና የምታውቀው ነገር የለም፡፡‹‹ማያውቁት ሀገር አይናፍቅም፡፡ ይባል የለ፤ እሷ እንደዛ የሆነባት ይመስለኛል፡፡ታዲያ አሁን ከማንጋ ነው የተገናኘችው? ከኤክስፐርት ጋር‹‹….እንዴ….እንዲህ ነው ለካ….ብላ እራሷን እንድትጠይቅ ካደረጋት በቂ ነው….እርግጠኛ ነኝ ደግሞ እሷም አንተ ያስብከውን ነገር ታስባለች…ወንድምህ ሴት አንደማያበረክት….ፍቅር ሳይሆን ወሲብ አሳዳጅ እንደሆነ ታውቃልች..ያ ማለት ከእሱ ጋር ዘላቂ ነገር እንደማይኖራት ቀድማም ስለምታስብ ያን ያህል አትጎዳም፡፡
‹‹የእኔ ባለቤት…..ኤክስፐርት እኮ ነሽ..አሁን አረጋጋሺኝ››አለና ከንፈሯን ሳማት፡፡ተቃቅፈው ተኙ..በጣም ደክሟቸው ስለነበረ በፍጥነት ነው በእንቅልፍ የተሸነፉት፡፡
///
ልክ ሀይሌ ሪዞርት ደርሶ መኪናውን እዳቆመ‹‹በቃ አሁን እኔ ልሂድ››አለችው፡፡
‹‹እንዴ በፍፅም ..ክፍሌ አስገብተሸኝ ነው ምትሄጂው››አላት፡፡
‹‹ለምን ክፍልህ ማስገባት ብቻ …አባብዬህ አስተኝቼህ ብሔድ አይሻልም?››አላገጠችበት፡፡
‹‹አዎ ይሻላል..ልብ አድርጊ ቃል ገብተሻል››
‹‹ምንድነው ቃል የገባሁት?››
‹‹..ቀኑን ሙሉ ከእኔ ስትደበቂና ስትሸሺ የዋልሺው ሳየንስ..አሁን አታበሳጪኛ ››ብሶቱን ቀሰቀሰችበት፡፡
‹‹ከአንተ አልተደበቅኩም ነበር››አለችው፡፡
አገጯን ይዞ ፊቷን በትኩረት እየተመለከተ ‹‹ምን አይነት ጫዋታ ነው የምትጫወቺው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹መጀመሪያ በጣም እስክግል ድረስ ትጠጊኛለሽ… ከዛ ትሮጪያለሽ። ››
ፊቷ ቀላ…ቃል እንኳን መናገር አቅቷት…አይኖቾን አፍጥጣ ልምምጥ በመሰለ
አስተያት እየተመለከተችው ነው፡፡እሱ ንግግሩን ቀጠለ‹እንግዲህ እኔን ለመግፋት ጠንክረሽ መጫወትሽን አቁሚ››ብሎ ከንፈሩን ወደከንፈሯ በጣም አስጠጋ፡፡ ሰውነቷ እየተንቀጠቀጠ እጆቿን ጠንካራ ጡንቻዎች ላይ ዘረጋች። እጆቹ ወገቧ ላይ ተጣበቁ፣ ወደእቅፉ እየተጣደፉች ተሳበች፣ ሙቀቱ እንደኤሌክትሪክ ንዝረት በመላ ሰውነቷ ተሰራጨ፡፡
በተስፋ መቁረጥ‹‹ሙሉ ትኩረትህን አልፈልግም››አለችው፡፡ ነገር ግን
ከአንደበቷ እየሾለኩ የሚወጡ ቃላቶቹ እስትንፋስ የሌላቸው እና የማያሳምኑ ነበሩ፣ በወጥመድ እንደተያዘች እና ክንፏ እንደተነቃቀለ ወፍ ደካማና በቁጥር ስር እንደዋለች አምናለች፡፡ ለበርካታ ደቂቃዎች እዛው ከመኪና ሳይወርዱ ሲሳሳሙና ሲላላሱ ቆዩ…ከዛ ጎትቶ ከመኪናው አወረዳት…ክንዷን ይዞ ወደመኝታ ክፍሉ ሲመራት ሳትቃወም ተከተለችው፡፡ልዩና ዘመናዊ ክፍል ነው ይዞት የገባው እሷ ግን ቀልቧ ሁሉ እሱ ላይ ስለነበር ለሌላው ነገር ግድ አልነበራትም፡፡
በራፉን መልሶ ዘጋና እዛው መሀል ወለል ላይ እንደቆመች ይስማት ጀመር…እንደምንም ከንፈሯን አላቀቀችና‹‹ የእኔ ቤት ከዚህ ብዙም የራቀ አይደለም… አስራአምስት ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው።›› አለችው፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ…ምንድነው ያሳቀህ?››
‹‹በጣም ነው እንጂ የሚያስቀው…ማንም ሴት እንዲህ አይነት መደራደሪያ አቅርባልኝ አታውቅም››
‹‹እኔ እኔ ነኝ ..ስለሌሎች ሴቶች አላውቅም፡፡››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ አለሽ እንዴ?››በአእምሮ ሲያብሰለስል የነበረው ጥያቄ ጠየቃት፡፡
አፈጠጠችበት..ደነገጠም ..ግራ ተጋባም
‹‹እንዴ …ምን መጥፎ ነገር ተናገርኩ?››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ ቢኖረኝ እዚህ ከአንተ ጋር ምን ያንዘላዝለኛል?፡፡››
ወደራሱ ጎተተና ከንፈሯ ላይ ተጠጣበቀባት…ተቃውሞ አላሰማችም..እንደውም ቀስ ብላ እጆቾን አነሳችና በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመች…አልጋውን ለቃ እየተንሳፈፈች እንደሆነ አይነት ምትሀታዊ አይነት ስሜት እየተሳማት ነው፡፡
የልቧን ምት ፍጥነት መቆጣጠር ስላልቻለችና መተንፈስም ስለከበዳት እየፈለገች ግን ከንፈሯን ከከንፈሩ አላቀቀችና
፣‹‹የሚጠጣ ነገር ይኖራል?››
ስትል ጠየቀችው፡፡መጠጥ የጠየቀችው በወሲብ ወቅት ድፍረት ይሰጣል ሲባል ስለሰማች ነው፡፡
‹‹አዎ አለ፡፡››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ… ለእሱም ለእሷም መጠጥ ይዞ መጣና ጠረጴዛውን ወደ አልጋው አስጠግቶ ከጎኗ ተመልሶ ቁጭ አለ፡፡
‹‹ምነው ይሄን ያህል አስፈራለሁ እንዴ?››
‹‹አይ በፍፅም…..ግን ››ንግግሯን አቋረጠችና ስልኳን ካስቀመጠችበት ኮመዲኖ ተንጠራርታ አነሳችና..ከፍታ ሰጠችው፡፡
‹‹ምንድነው?››
ተቀበላትና ተመለከተ..ውብ ቆንጅዬ የምታምር ልጅ ፎቶ ይታያል፡፡ግራ ገባውና ቀና ብሎ በትኩረት አያት‹‹ልጄ ነች…ስድስት አመቷ ነው፡፡››
‹‹ምን …?››ከተቀመጠበት ተነሳ…አፍጥጦ ፎቶውን መመለክት ጀመረ፡፡
በሁኔታው ተበሳጨች….‹‹… ዝም ብዬ እንድታውቀው ስለፈለኩ ነው እንጂ ይሄን ያህል ምን ያስደነግጥሀል…?አታገባኝ ወይ አትወሽመኝ ..አንድ ልጅ ኖረኝ አምስት ምን አጨናነቀህ…?››
በቆመበት አፍጥጦ በዝምታ ያያት ጀመር፡፡ያ ደግሞ የበለጠ ንዴቷን እንዲጨምር አደረገ…‹‹እንደውም ሁሉ ነገር እዚህ ላይ ያብቃ ወደቤቴ ልሂድ››ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ተንደርድሮ መጥቶ ትከሻዋን ይዞ አስቀመጣትና ግንባሯን ሳማት፡፡
‹‹በጣም ነጭናጫ ሴት መሆንሽን ታውቂያለሽ?››
‹‹እንኳን››
‹‹እኔ ይህቺን የመሰለች ልጅ ስላለሽ ቀናሁብሽ እንጂ አልተበሳጨሁበሽም…በጣም እኮ ነው የምታምረው…..ደግሞ በስንት አመትሽ ብትወልጂያት ነው እንዲህ ያደገችው?››
‹‹በ17››
‹‹እና የት ነው ያለችው ..ከአንቺ ጋር ወይስ አባቷ ጋር?››
‹‹አባቷ መፀናሷን እንዳወቀ ነው ሸሽቶ ውትድርና ተቀጥሮ የጠፋው..እስከአሁን ይኑር ይሙት አላውቅም…እሷ ከእኔ ጋር ነው ያለችው፡፡››
‹‹እና አሁን እቤት ነው ያለቻ ?ብንሄድ እናገኛታለን?››
በመገረም አፍጥጣ ተመለከተችው‹‹የእውነት አሁን እንሂድ ብልህ ትሄዳለህ?››
‹‹አዎ..››ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ …‹‹ሰዓቱ ገና ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ከ10 ነው …ተነሽ እንደውም….የሆነ ነገር ገዝተንላት እንሂድ እና እናስደስታት፡፡››
እሱ ጃኬቱን ሲለብስ እሷ ከተቀመጠችበት ሳትንቀሳቀስ በገረሜታ አፏን ከፈተችና በፍዘት ታየው ነበር፡፡
‹‹አልሰማሺኝም እንዴ? ተነሽ እንሂድ››
‹‹ልጅ ማትወድ መስሎኝ ነበር››
በተራው ደነገጠ…‹‹እንዴ ምን ማለት ነው…?እንዴት እንደዛ ልታስቢ ቻልሽ?››
‹‹ቅድም የወንድምህን ልጅ ወደአንተ ይዤ መጥቼ ሳስተዋውቅህ..ከእቅፌ ወስደህ አቅፈህ የምትስመው መስሎኝ ነበር…ግን እንደዛ አላደረክም..ጉንጩን አንኳን አልሳምክም››
ወደእሷ መጣና ከጎኗ ተቀመጠ‹‹ያን ያህል ስትታዘቢኝ ነበር ማለት ነው…?ላቅፈውና ልስመው በጣም ነበር የፈለኩት….አጎትህ ነኝ ብዬ እሽኮኮ በማድረግ ከሆቴሉ ይዤው ወጥቼ ላዝናናው ሁሉ ፈልጌ ነበር..ግን አልቻልኩም…ምክንያቱም የወንድሜ ልጅ ነው ፤ስለወንድሜ ሳስብ ደግሞ በደረቷ ቢላዋ ተሰክቶባት ወለል ላይ የተዘረጋች እናቴና በገመድ የተንጠለጠለች እህቴ ነች ወደአእምሮዬ የምትመጣው…በዛን ወቅት አሰብ የነበረው ስለእነሱ ነበር …እንባዬ እንዳያመልጠኝና በሰርግ እድምተኞች ፊት እንዳልዋረድ እየጣርኩ ነበር››እንባው ከአይኖቹ እየተዘረገፈ መውረድ ጀመረ፡፡ ደነገጠችና ከተቀመጠችበት ተነሳች በእጇቾ እንባውን እበሰችና ግንበሩን ጉንጮቹን እያገላበጠች እየሰማች‹‹ይቅርታ…በጣም ይቅርታ…እኔ እንዲህ አይነት ቀሽም ሴት ነኝ…ሶሪ ወንዶችን ሰላማላምን ሁሉን ነገር ነው የምጠራጠረው…ከልጄ አባት ውጭ ሌላ ወንድ አላውቅም…ከአንተ ጋር በእንደዚህ አይነት መጠን መቀራረብና በአንድ ክፍል ውስጥ መሆን በጣም ቢያስደስተኝም በዛው መጠን አስፈርቶኛል….ለዛ ነው ያልሆነ ነገር የምቀባጥረው፡፡››
‹‹ችግር የለውም… ተረድቼሻለው››
‹‹በቃ በፈጣሪ ያልኩህን ሁሉ እርሳው…››ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት..በጠንካራ እጆቹን በቀጭን ወገቧ ዙሪያ ጠመጠመና ከሰውነት ጋር ለጥፎ ትንፋሽ እስኪያጥራት መጠጣት…..ከዛ ለቀቃትና..‹‹በይ አታረሳሺኝ ተነሽ እንሂድ››
‹‹በእውነት ቢሆንና ብታይህ በጣም ነበር የምትደሰተው…ሙዚቀዎችህን በጣም ነው የምትወዳቸው…ግን አሁን የለችም››
‹‹የለችም ማለት?››
‹‹አሁን ክረምት አይደል..ትምህርት ስለተዘጋ አያቶቾ ወስደዋታል….የሚቀጥለውን አንድ ወር እነሱ ጋር ነው የምታሳለፈው….››
‹‹እ ያሳዝናል…እንግዲህ ምን ማድረግ ይቻላል ስትመለስ ታስተዋውቂኛለሽ››
‹ስትመለስ?››አለችና ሳቀች፡፡
‹‹ምን ያስቅሻል?››
‹‹የዛሬ ወር እኮ ነው ያልኩህ…››
‹‹ምነው የዛሬ ወር የለሁም እንዴ..?አለሁ እኮ ፤ማለቴ በፍቅርሽ አሟሙተሸ ካላጠፋሺኝ አለው..››
‹‹ይሁን እስኪ…..ለማንኛውም አስገርመሀኛል››አለችና የመጠጡን ብርጭቆ አነስታ ተጎነጨች፡፡
‹‹እድሉን እስከሰጠሺን ድረስ ገና ብዙ አሰግርምሻለው፡፡››
ከዛ ቀልል ያለ ወሬ እያወሩ ከመጠጡ መጎንጨታቸውን ቀጠሉ….
‹‹ይሞቃል አይደል?››አለችው የእውነትም በጣም እየሞቃት ነው…ያላወቀችው የሙቀቱ ምንጭ ከምትጠጣው መጠጥ ይመንጭ ወይም ከጎኗ ካለው ሸበላ ወይም ከአየር ፀባዩ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡
‹‹እኔም ሞቋኛል …››አለና ጃኬቱን አወለቀ፡፡
‹‹እኔስ ቀሚሴን ላውልቅ?››አለችውና ሳቀች፡፡
‹‹ይቻላል..ቆይ እንደውም..›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ወደሻንጣው በመሄድ ከፈተው፡፡ምን ሊያደርግ ነው ብላ በትኩረት እየተከታተለችው ነው፡፡
ስስ ቁምጣ እና ቲሸርት አወጣና…እንቺ ቀሚሱን አውልቂና ይሄን ልበሺ አለና ለራሱ ሌላ ቢጃማ በማውጠት ሱሪውን ለማውለቅ ቀበቷውን መፍታት ጀመረ፡፡
‹‹ምን እያደረክ ነው?››
‹‹ሱሬዬን ልቀይር ነዋ….››
ሱሪውን ወደታች አወለቀ..ከዛ ከላይ የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ..በነጭ ፓካውትና በሰማያዊ ፓንት ብቻ በሁለት ሜትር ርቀት ቆሞ ስትመለከት ሰውነቷን ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ነገር አንዘረዘራት፡፡በልብስ ከሚታየው ይልቅ እርቃኑን ያምራል…ደግሞ ከፊል ሰውነቱ በተለያዩ ማራኪ ንቅሳቶች የተዥጎረጎረ ነው፡፡
‹‹ምነው ፈዘዝሽ?››ብሎ አሳፈራት፡፡
‹‹ምን ፈዛለው…እንደ ሸራ በስእል ተዥጎርጉረህ የለ እንዴ?››
የሚቀይረውን ቢጃማ ሱሪ አነሳና በእጁ እንደያዘ‹‹ያምራል አይደል…?እስኪ በደንብ ተመልከቺው ››አለና ይበልጥ ወደእሷ ተጠጋና ስሯ ቆመ፡፡
ዝም አለች ..ጎትቶ አስነሳት‹‹እንዴ ምን እያደረክ ነው?››
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
‹‹ነይ እስኪ ቁጭ እንበል›› አለና ክንዷን ይዞ እየጎተተ አልጋው ጠርዝ ላይ አስቀመጣት፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ…ምንድነው ያሳቀህ?››
‹‹በጣም ነው እንጂ የሚያስቀው…ማንም ሴት እንዲህ አይነት መደራደሪያ አቅርባልኝ አታውቅም››
‹‹እኔ እኔ ነኝ ..ስለሌሎች ሴቶች አላውቅም፡፡››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ አለሽ እንዴ?››በአእምሮ ሲያብሰለስል የነበረው ጥያቄ ጠየቃት፡፡
አፈጠጠችበት..ደነገጠም ..ግራ ተጋባም
‹‹እንዴ …ምን መጥፎ ነገር ተናገርኩ?››
‹‹ባል ወይም ፍቅረኛ ቢኖረኝ እዚህ ከአንተ ጋር ምን ያንዘላዝለኛል?፡፡››
ወደራሱ ጎተተና ከንፈሯ ላይ ተጠጣበቀባት…ተቃውሞ አላሰማችም..እንደውም ቀስ ብላ እጆቾን አነሳችና በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመች…አልጋውን ለቃ እየተንሳፈፈች እንደሆነ አይነት ምትሀታዊ አይነት ስሜት እየተሳማት ነው፡፡
የልቧን ምት ፍጥነት መቆጣጠር ስላልቻለችና መተንፈስም ስለከበዳት እየፈለገች ግን ከንፈሯን ከከንፈሩ አላቀቀችና
፣‹‹የሚጠጣ ነገር ይኖራል?››
ስትል ጠየቀችው፡፡መጠጥ የጠየቀችው በወሲብ ወቅት ድፍረት ይሰጣል ሲባል ስለሰማች ነው፡፡
‹‹አዎ አለ፡፡››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ… ለእሱም ለእሷም መጠጥ ይዞ መጣና ጠረጴዛውን ወደ አልጋው አስጠግቶ ከጎኗ ተመልሶ ቁጭ አለ፡፡
‹‹ምነው ይሄን ያህል አስፈራለሁ እንዴ?››
‹‹አይ በፍፅም…..ግን ››ንግግሯን አቋረጠችና ስልኳን ካስቀመጠችበት ኮመዲኖ ተንጠራርታ አነሳችና..ከፍታ ሰጠችው፡፡
‹‹ምንድነው?››
ተቀበላትና ተመለከተ..ውብ ቆንጅዬ የምታምር ልጅ ፎቶ ይታያል፡፡ግራ ገባውና ቀና ብሎ በትኩረት አያት‹‹ልጄ ነች…ስድስት አመቷ ነው፡፡››
‹‹ምን …?››ከተቀመጠበት ተነሳ…አፍጥጦ ፎቶውን መመለክት ጀመረ፡፡
በሁኔታው ተበሳጨች….‹‹… ዝም ብዬ እንድታውቀው ስለፈለኩ ነው እንጂ ይሄን ያህል ምን ያስደነግጥሀል…?አታገባኝ ወይ አትወሽመኝ ..አንድ ልጅ ኖረኝ አምስት ምን አጨናነቀህ…?››
በቆመበት አፍጥጦ በዝምታ ያያት ጀመር፡፡ያ ደግሞ የበለጠ ንዴቷን እንዲጨምር አደረገ…‹‹እንደውም ሁሉ ነገር እዚህ ላይ ያብቃ ወደቤቴ ልሂድ››ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡ተንደርድሮ መጥቶ ትከሻዋን ይዞ አስቀመጣትና ግንባሯን ሳማት፡፡
‹‹በጣም ነጭናጫ ሴት መሆንሽን ታውቂያለሽ?››
‹‹እንኳን››
‹‹እኔ ይህቺን የመሰለች ልጅ ስላለሽ ቀናሁብሽ እንጂ አልተበሳጨሁበሽም…በጣም እኮ ነው የምታምረው…..ደግሞ በስንት አመትሽ ብትወልጂያት ነው እንዲህ ያደገችው?››
‹‹በ17››
‹‹እና የት ነው ያለችው ..ከአንቺ ጋር ወይስ አባቷ ጋር?››
‹‹አባቷ መፀናሷን እንዳወቀ ነው ሸሽቶ ውትድርና ተቀጥሮ የጠፋው..እስከአሁን ይኑር ይሙት አላውቅም…እሷ ከእኔ ጋር ነው ያለችው፡፡››
‹‹እና አሁን እቤት ነው ያለቻ ?ብንሄድ እናገኛታለን?››
በመገረም አፍጥጣ ተመለከተችው‹‹የእውነት አሁን እንሂድ ብልህ ትሄዳለህ?››
‹‹አዎ..››ሞባይሉን አወጣና ሰዓቱን ተመለከተ …‹‹ሰዓቱ ገና ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ከ10 ነው …ተነሽ እንደውም….የሆነ ነገር ገዝተንላት እንሂድ እና እናስደስታት፡፡››
እሱ ጃኬቱን ሲለብስ እሷ ከተቀመጠችበት ሳትንቀሳቀስ በገረሜታ አፏን ከፈተችና በፍዘት ታየው ነበር፡፡
‹‹አልሰማሺኝም እንዴ? ተነሽ እንሂድ››
‹‹ልጅ ማትወድ መስሎኝ ነበር››
በተራው ደነገጠ…‹‹እንዴ ምን ማለት ነው…?እንዴት እንደዛ ልታስቢ ቻልሽ?››
‹‹ቅድም የወንድምህን ልጅ ወደአንተ ይዤ መጥቼ ሳስተዋውቅህ..ከእቅፌ ወስደህ አቅፈህ የምትስመው መስሎኝ ነበር…ግን እንደዛ አላደረክም..ጉንጩን አንኳን አልሳምክም››
ወደእሷ መጣና ከጎኗ ተቀመጠ‹‹ያን ያህል ስትታዘቢኝ ነበር ማለት ነው…?ላቅፈውና ልስመው በጣም ነበር የፈለኩት….አጎትህ ነኝ ብዬ እሽኮኮ በማድረግ ከሆቴሉ ይዤው ወጥቼ ላዝናናው ሁሉ ፈልጌ ነበር..ግን አልቻልኩም…ምክንያቱም የወንድሜ ልጅ ነው ፤ስለወንድሜ ሳስብ ደግሞ በደረቷ ቢላዋ ተሰክቶባት ወለል ላይ የተዘረጋች እናቴና በገመድ የተንጠለጠለች እህቴ ነች ወደአእምሮዬ የምትመጣው…በዛን ወቅት አሰብ የነበረው ስለእነሱ ነበር …እንባዬ እንዳያመልጠኝና በሰርግ እድምተኞች ፊት እንዳልዋረድ እየጣርኩ ነበር››እንባው ከአይኖቹ እየተዘረገፈ መውረድ ጀመረ፡፡ ደነገጠችና ከተቀመጠችበት ተነሳች በእጇቾ እንባውን እበሰችና ግንበሩን ጉንጮቹን እያገላበጠች እየሰማች‹‹ይቅርታ…በጣም ይቅርታ…እኔ እንዲህ አይነት ቀሽም ሴት ነኝ…ሶሪ ወንዶችን ሰላማላምን ሁሉን ነገር ነው የምጠራጠረው…ከልጄ አባት ውጭ ሌላ ወንድ አላውቅም…ከአንተ ጋር በእንደዚህ አይነት መጠን መቀራረብና በአንድ ክፍል ውስጥ መሆን በጣም ቢያስደስተኝም በዛው መጠን አስፈርቶኛል….ለዛ ነው ያልሆነ ነገር የምቀባጥረው፡፡››
‹‹ችግር የለውም… ተረድቼሻለው››
‹‹በቃ በፈጣሪ ያልኩህን ሁሉ እርሳው…››ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት..በጠንካራ እጆቹን በቀጭን ወገቧ ዙሪያ ጠመጠመና ከሰውነት ጋር ለጥፎ ትንፋሽ እስኪያጥራት መጠጣት…..ከዛ ለቀቃትና..‹‹በይ አታረሳሺኝ ተነሽ እንሂድ››
‹‹በእውነት ቢሆንና ብታይህ በጣም ነበር የምትደሰተው…ሙዚቀዎችህን በጣም ነው የምትወዳቸው…ግን አሁን የለችም››
‹‹የለችም ማለት?››
‹‹አሁን ክረምት አይደል..ትምህርት ስለተዘጋ አያቶቾ ወስደዋታል….የሚቀጥለውን አንድ ወር እነሱ ጋር ነው የምታሳለፈው….››
‹‹እ ያሳዝናል…እንግዲህ ምን ማድረግ ይቻላል ስትመለስ ታስተዋውቂኛለሽ››
‹ስትመለስ?››አለችና ሳቀች፡፡
‹‹ምን ያስቅሻል?››
‹‹የዛሬ ወር እኮ ነው ያልኩህ…››
‹‹ምነው የዛሬ ወር የለሁም እንዴ..?አለሁ እኮ ፤ማለቴ በፍቅርሽ አሟሙተሸ ካላጠፋሺኝ አለው..››
‹‹ይሁን እስኪ…..ለማንኛውም አስገርመሀኛል››አለችና የመጠጡን ብርጭቆ አነስታ ተጎነጨች፡፡
‹‹እድሉን እስከሰጠሺን ድረስ ገና ብዙ አሰግርምሻለው፡፡››
ከዛ ቀልል ያለ ወሬ እያወሩ ከመጠጡ መጎንጨታቸውን ቀጠሉ….
‹‹ይሞቃል አይደል?››አለችው የእውነትም በጣም እየሞቃት ነው…ያላወቀችው የሙቀቱ ምንጭ ከምትጠጣው መጠጥ ይመንጭ ወይም ከጎኗ ካለው ሸበላ ወይም ከአየር ፀባዩ እርግጠኛ መሆን አልቻለችም፡፡
‹‹እኔም ሞቋኛል …››አለና ጃኬቱን አወለቀ፡፡
‹‹እኔስ ቀሚሴን ላውልቅ?››አለችውና ሳቀች፡፡
‹‹ይቻላል..ቆይ እንደውም..›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ወደሻንጣው በመሄድ ከፈተው፡፡ምን ሊያደርግ ነው ብላ በትኩረት እየተከታተለችው ነው፡፡
ስስ ቁምጣ እና ቲሸርት አወጣና…እንቺ ቀሚሱን አውልቂና ይሄን ልበሺ አለና ለራሱ ሌላ ቢጃማ በማውጠት ሱሪውን ለማውለቅ ቀበቷውን መፍታት ጀመረ፡፡
‹‹ምን እያደረክ ነው?››
‹‹ሱሬዬን ልቀይር ነዋ….››
ሱሪውን ወደታች አወለቀ..ከዛ ከላይ የለበሰውን ሸሚዝ አወለቀ..በነጭ ፓካውትና በሰማያዊ ፓንት ብቻ በሁለት ሜትር ርቀት ቆሞ ስትመለከት ሰውነቷን ኤሌክትሪክ እንደጨበጠ ነገር አንዘረዘራት፡፡በልብስ ከሚታየው ይልቅ እርቃኑን ያምራል…ደግሞ ከፊል ሰውነቱ በተለያዩ ማራኪ ንቅሳቶች የተዥጎረጎረ ነው፡፡
‹‹ምነው ፈዘዝሽ?››ብሎ አሳፈራት፡፡
‹‹ምን ፈዛለው…እንደ ሸራ በስእል ተዥጎርጉረህ የለ እንዴ?››
የሚቀይረውን ቢጃማ ሱሪ አነሳና በእጁ እንደያዘ‹‹ያምራል አይደል…?እስኪ በደንብ ተመልከቺው ››አለና ይበልጥ ወደእሷ ተጠጋና ስሯ ቆመ፡፡
ዝም አለች ..ጎትቶ አስነሳት‹‹እንዴ ምን እያደረክ ነው?››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡
ይህ ምሽት ከዘሚካኤል ጋር በፍቅር ከመውደቅ ጋር ወይም ከእሱ ጋር የወደፊት ከህልም ከማለም ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። እና ሁሉም ነገር የሚከናወነው ለአካላዊ ደስታ ብቻ ተብሎ ነው። የልጅነት ፍቅረኛዋ ለዚህ ሁሉ አመታት የሆነ ነገሯን ሰርቆባታል እና አሁን ሊመልስላት ይገባል ። እና ጉዳዩ ያ ብቻ ነበር።
ጠረጴዛ ላይ ያለው ብርጭቆ አነሳና ከተጎነጨለት በኋላ እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነባት ፡፡
፤ዝም አለች…እጁን በአንገቷ ዙሪያ አሻግሮ በቲሸርቱ ስር አሾለከና ወደጡቷ መጓዝ ጀመረ..ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹ዘና በይ እንጂ። ይህ ለሁለታችንም ጥሩ ይሆናል፣ ቃል እገባልሻለው።›› መልሶ እጁን አወጣና ወደአልጋው ላይ ቀድሟት በመውጣት እጇን ይዞ ወደ አልጋው እየሳበ ።
‹‹ተነሽ በቃ እንተኛ። ››አላት፡፡
ዝም ብላ ተጎተተችለትና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋው ላይ ወጣች ።መናገር አልቻለችም፣ የልቧ ፈጣን ምቶች በጉሮሮዋ ላይ ተስፈንጥረው ሚወጡ ይመስላሉ።ወደራሱ ሳበና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡እና እጆቹን ፀጉሯ ውስጥ አስገባና ይልግላት ጀመር…ከመደንዘዞ የተነሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡ከዛ አንገቷን ..ጆሮዋን መሳም ጀመረ …ቃተተች.፡፡ወደታች ዝቅ አለና ቲሸርቷን ገለጠና ከእንብርቷ ጀምሮ እየላሰ ወደላይ ወጣ…ጡቶቾ ጋር ደረሰ የቀኝ ጡቷን ጫፍ በምላሱ እየላሰ የግራውን ጡቷን በእጆቹ እየጨመቀ ያፍተለትላት ጀመር…በፈጣሪ… እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን በፍፁም አታውቅም….ጡት ለተሳማ እንዴት ነው መላ ሰውነት እንዲህ ቀልጦ የሚንሳፈፈው…?.በጣም ያስገረማት ጉዳይ ነው፡፡
‹‹ እሺ በቃ አሁን….››ተንተባተበችና እንደምንም ጨክና ከጡቷ አላቀቀችው
‹‹እስከ ሞት ድረስ የፈራሽ ትመስያለሽ። ምንድነው ችግሩ?፧››ሲላት እንደምንም እያጎለበተችው የነበረው ትንሹ ድፍረት ጥሏት ሄደ…ይሄንን ደግሞ እሱም በግልፅ ማየት ይችላል…፡፡
‹‹መብራቶቹን ማጥፋት እንችላለን?››ብላ በሹክሹክታ ጠየቀችው።
‹‹አላደርገውም።…ውብ እርቃኗን ለማያት ለቀናት ስለእሷ ሳሰላስል የሰነበትኩላትን ልጅ ሳገኛት …በጭለማ….አይ አይሆንም ..አንቺን ለማግኘት ያን ሁሉ ጥረት የጣርኩት በጨለማ ውስጥ ፍቅር ለመስራት አይደለም።››ተቃወማት፡፡
ጡቶቿ ትንሽ ነበሩ፣ ዳሌዋ ጠባብ እና የልጅ ነበር። ጉንጯን ነካ፣ በዓይኑ ያልጠበቀችው ልስላሴ እና ፈገግታ ተመለከተች። ' ለመቃወም አፏን ከፈተች እሱ ግን ጣቱን ከንፈሯ ላይ አሳረፈ።‘
‹‹አትልፊ አልስማማም››አለና የዋናውን መብራት ማብሪያ / ማጥፊያ ለማጥፋት አልጋውን ለቅቆ ወረደ , ደማቁን ብርሀን ቢወገድም አረንጓዴና ደብዛዛ ብርሀን ግን አሁንም ቤቱን እንደሞላው ነው፡፡ ከላይ የለበሰውን ካኔቴራ አወለቀና እርቃኑን ወደአላጋው ላይ ወጣ…..እና ቆመ….‹‹ምነው ቁጭ በል እንጂ››
…
የለበሰውን ቁምጣ ከነፓንቱ አንድ ላይ መዥርጦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….እንደሀውልት የተገተረው እንትኑ አይኗቾን ተቆጣጠረ…..የበለጠ በፍርሀት ተንዘረዘረች፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንዴ ምን ሰራለሁ.. ልንተኛ አይደል ….?ብርድልብሱን እና አንሶላውን ገለጠና ከውስጥ ገባ…
.‹‹አውልቀሽ ወደእኔ ትመጪያለሽ ወይስ…..?››
ምንም መናገር አልቻለችም….ዝም አለች፡፡‹‹ምንም ልምድ የለሽም አይደል?››ሲል ጠየቃት፡፡፡
‹‹ልክ ነህ። በዚህ ረገድ ብዙ ልምድ የለኝም። እንደውም እውነቱ ለመናገር እኔ ምንም አይነት ልምድ የለኝም ›› አለችው ። ማስመሰል ምን ፋይዳ አልነበረው? ከአመታት በፊት ካጋጠማት ከዛ አስጸያፊ ምሽት ገጠመኞ በኋላ በእድሜ ጨምራ እና በስሜት ጎልምሳ ሊሆን ይችላል… ግን ያ በቂ አይሆንም። ለዛውም እንደ ዘሚካኤል አይነት ከሴት ጋር ባለው ልምድ የበለፀገ አይነት ሰውን ለመቋቋም ፈጽሞ እንደማትችል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹ከብዙ ልምድ ያላቸው ሴቶች ጋር ተኝተሀል ..እና ከእኔ ጋር በምታደርገው ነገር ቅር መሰኘትህ አይቀርም ፣ ››ብላ ጨረሰች ።ሙሉ በሙሉ ተሸነፈች።
‹‹ ውዴ ፣ ስለ እንደዛ አይነት ነገር ፈፅሞ መጨነቅ አያስፈልግሽም -ሁሉን ነገር አብረን በዝግታና በትግስት እናደርገዋለን….እኔ አንቺን ከማንም ጋር ላወዳድርሽ ሀሳብ የለኝም….›› የእሱ አጽናኝና አበረታች ቃላት ጉዳቷን እና ውርደቷን ትንሽ አጠበላት።ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይህ ፈተና አይደለም.›› ጎተተና ወደውስጥ ስቦ አስገባት፡፡ከዛ ቀስ አለና ቲሸርቷን ወደላይ ስቦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….ከዛ ወደኋላ አጋዳማትና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡
‹‹እንግዲህ እጅ ሰጥቻለው…ችግር የለውም ካልክ….እንደፈለክ አድርገኝ››በማለት ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠቷን በይፋ አወጀች፡፡
‹‹ ውዴ አፈጻጸም ላይ ጭንቀት ካለብሽ ለምንድነው ለተወሰነ ጊዜ ሂደቱን የማትመሪው?››የሚል አስገራሚ ሀሳብ አቀረበላት፡፡
በድንገት መተንፈስ አቃታት።
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ..?ጭራሽ መምራት…‹‹በል የምታደርገውን እንደፈለግክ አድርግ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ደግሞ እኔም አንቺ የምታስቢውን ያህል ጎበዝ ላልሆን እችላለው ›› ብሎ ቀጠለ፣ በብልህ ጣቶቹን ጡቷቿን እያፍተለተለ ነው፡ ፡ቃተተች፡፡እሱ ሹክሹክታ በመሰለ ድምፅ መናገሩን ቀጠለ፡፡
ተንቀጠቀጠች፡፡ከአንገቷ ጀምሮ ወደታች ይልሳት ጀመር …ሳታስበው ሰውነቱ ላይ ተጣበቀችበት….ከታች እንትኑ ክፉኛ ቆረቆራት..ደስ የሚል መቆርቆር….የሚበላ እና ሚያሳክክ አይነት መቆርቆር …እሱም እንደተመቻት ስለገባው ይሰመስላል… በጠንካራ ጡንቻው ሰቅስቆ ወደራሱ አጥብቆ መሳሙን ቀጠለ….እያንዳንዷ የሚስማት ቦታ ልዩ አይነት የተለያየ ጣእም ያለው መስሎ ተሰማት…..ለዘመናት እንደዛ እየሳማት እንዲቆይ ተመኘች….እየቀለጠች ነው….ሆዷና ጀርባዋ በላብ እየታጠበ ነው፡፡እጁን ወደታች ሰደደና በለበሰችው ቁምጣዋንና ፓንቷን ሰቅስቆ ገባ……..‹‹ወይኔ ጉዴ ምን ሊያደርግ ነው?››አሰበች …የእጁን መዳፍ ብልቷ ላይ አሳረፈ……ድምፅ አውጥታ ማቃሰት ጀመረች….ከላዮ ላይ ተነሳና ቀና ብሎ የለበሰችውን ቁምጣን ፓንቷን አንድ ላይ ይዞ ወደታች ጎትቷ ማውለቅ ጀመረ…እግሯን ወደላይ ከፍ በማድረግ ተባበረችው፡፡ወደ ሰውነቱ አጥብቆ አቀፋትና ከጆሮዋ አንስቶ አንገቷን መሳም ጀመረ….ተቁነጠነጠች፡፡ቀስ እያለ መሳሙንም መዳበሱንም ሳያቋርጥ ወደታች ሄደ… ከዛ አንገቱን እግሯቾ መካከል ደፈቀ….ለፈለፈች….በመላ ሰውነቷ ቤንዚል ተርከፍክፎ ክብሪት የተጫራባት ነው የመሰላት…እጆቾን ፀጉሩ ላይ አድርጋ ታሻሸው ጀመር…ቀስ አለና እየሳማት ወደላይ መጓዝ ጀመረ… ከንፈሯ ጋር ሲደርስ ቀድማ ተጣበቀችበት….ሙሉ በሙሉ እግሮቾን መካከል ገብቷ ተዋሀዳት….ልዩ ጣፋጭነት ያለው ስቃይ ተሰማት…ስቃዩ እንዲያቆም ግን ፈፅሞ አትፈልግም…ይበልጥ መቃተት ይበልጥ መሰቃየት ፈልጋለች፡፡ሁለቱም እኩል ከፍተኛ ፍንዳታ ላይ ደረሱ አደኛው ሌለኛውን ወደራሳቸው ጨምቀው አቀፉ..ተርገፈገፉ…..በመከራ ተላቀቁና ጎን ለጎን ተዘረሩ፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ወደእሷ ዞረና‹‹እንዴት ነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አረ…እንዲህ አይነት ጉብዝና መኖሩን እራሱ የት አውቃለው?››አለችው፡፡
ግንባሩን ወደ እርስዋ አስጠጋ ፣በረጅሙ ተነፈሰች።‹‹የእኔ ቆንጆ ሁለነገርሽ እንደሚያምር ታውቂያለሽ አይደል?...አይዞሽ ሁሉ ነገር ልዩ ይሆናል…ወደፊት ብዙ የምትማሪው ነገር ሊኖር ይችላል›› አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
‹‹በቃ አትንዘላዘልብኝ ..ልበስ››ኮስተር አለችበት፡፡
ይህ ምሽት ከዘሚካኤል ጋር በፍቅር ከመውደቅ ጋር ወይም ከእሱ ጋር የወደፊት ከህልም ከማለም ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረውም። እና ሁሉም ነገር የሚከናወነው ለአካላዊ ደስታ ብቻ ተብሎ ነው። የልጅነት ፍቅረኛዋ ለዚህ ሁሉ አመታት የሆነ ነገሯን ሰርቆባታል እና አሁን ሊመልስላት ይገባል ። እና ጉዳዩ ያ ብቻ ነበር።
ጠረጴዛ ላይ ያለው ብርጭቆ አነሳና ከተጎነጨለት በኋላ እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነባት ፡፡
፤ዝም አለች…እጁን በአንገቷ ዙሪያ አሻግሮ በቲሸርቱ ስር አሾለከና ወደጡቷ መጓዝ ጀመረ..ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹ዘና በይ እንጂ። ይህ ለሁለታችንም ጥሩ ይሆናል፣ ቃል እገባልሻለው።›› መልሶ እጁን አወጣና ወደአልጋው ላይ ቀድሟት በመውጣት እጇን ይዞ ወደ አልጋው እየሳበ ።
‹‹ተነሽ በቃ እንተኛ። ››አላት፡፡
ዝም ብላ ተጎተተችለትና ሙሉ በሙሉ ወደ አልጋው ላይ ወጣች ።መናገር አልቻለችም፣ የልቧ ፈጣን ምቶች በጉሮሮዋ ላይ ተስፈንጥረው ሚወጡ ይመስላሉ።ወደራሱ ሳበና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡እና እጆቹን ፀጉሯ ውስጥ አስገባና ይልግላት ጀመር…ከመደንዘዞ የተነሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡ከዛ አንገቷን ..ጆሮዋን መሳም ጀመረ …ቃተተች.፡፡ወደታች ዝቅ አለና ቲሸርቷን ገለጠና ከእንብርቷ ጀምሮ እየላሰ ወደላይ ወጣ…ጡቶቾ ጋር ደረሰ የቀኝ ጡቷን ጫፍ በምላሱ እየላሰ የግራውን ጡቷን በእጆቹ እየጨመቀ ያፍተለትላት ጀመር…በፈጣሪ… እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን በፍፁም አታውቅም….ጡት ለተሳማ እንዴት ነው መላ ሰውነት እንዲህ ቀልጦ የሚንሳፈፈው…?.በጣም ያስገረማት ጉዳይ ነው፡፡
‹‹ እሺ በቃ አሁን….››ተንተባተበችና እንደምንም ጨክና ከጡቷ አላቀቀችው
‹‹እስከ ሞት ድረስ የፈራሽ ትመስያለሽ። ምንድነው ችግሩ?፧››ሲላት እንደምንም እያጎለበተችው የነበረው ትንሹ ድፍረት ጥሏት ሄደ…ይሄንን ደግሞ እሱም በግልፅ ማየት ይችላል…፡፡
‹‹መብራቶቹን ማጥፋት እንችላለን?››ብላ በሹክሹክታ ጠየቀችው።
‹‹አላደርገውም።…ውብ እርቃኗን ለማያት ለቀናት ስለእሷ ሳሰላስል የሰነበትኩላትን ልጅ ሳገኛት …በጭለማ….አይ አይሆንም ..አንቺን ለማግኘት ያን ሁሉ ጥረት የጣርኩት በጨለማ ውስጥ ፍቅር ለመስራት አይደለም።››ተቃወማት፡፡
ጡቶቿ ትንሽ ነበሩ፣ ዳሌዋ ጠባብ እና የልጅ ነበር። ጉንጯን ነካ፣ በዓይኑ ያልጠበቀችው ልስላሴ እና ፈገግታ ተመለከተች። ' ለመቃወም አፏን ከፈተች እሱ ግን ጣቱን ከንፈሯ ላይ አሳረፈ።‘
‹‹አትልፊ አልስማማም››አለና የዋናውን መብራት ማብሪያ / ማጥፊያ ለማጥፋት አልጋውን ለቅቆ ወረደ , ደማቁን ብርሀን ቢወገድም አረንጓዴና ደብዛዛ ብርሀን ግን አሁንም ቤቱን እንደሞላው ነው፡፡ ከላይ የለበሰውን ካኔቴራ አወለቀና እርቃኑን ወደአላጋው ላይ ወጣ…..እና ቆመ….‹‹ምነው ቁጭ በል እንጂ››
…
የለበሰውን ቁምጣ ከነፓንቱ አንድ ላይ መዥርጦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….እንደሀውልት የተገተረው እንትኑ አይኗቾን ተቆጣጠረ…..የበለጠ በፍርሀት ተንዘረዘረች፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንዴ ምን ሰራለሁ.. ልንተኛ አይደል ….?ብርድልብሱን እና አንሶላውን ገለጠና ከውስጥ ገባ…
.‹‹አውልቀሽ ወደእኔ ትመጪያለሽ ወይስ…..?››
ምንም መናገር አልቻለችም….ዝም አለች፡፡‹‹ምንም ልምድ የለሽም አይደል?››ሲል ጠየቃት፡፡፡
‹‹ልክ ነህ። በዚህ ረገድ ብዙ ልምድ የለኝም። እንደውም እውነቱ ለመናገር እኔ ምንም አይነት ልምድ የለኝም ›› አለችው ። ማስመሰል ምን ፋይዳ አልነበረው? ከአመታት በፊት ካጋጠማት ከዛ አስጸያፊ ምሽት ገጠመኞ በኋላ በእድሜ ጨምራ እና በስሜት ጎልምሳ ሊሆን ይችላል… ግን ያ በቂ አይሆንም። ለዛውም እንደ ዘሚካኤል አይነት ከሴት ጋር ባለው ልምድ የበለፀገ አይነት ሰውን ለመቋቋም ፈጽሞ እንደማትችል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹ከብዙ ልምድ ያላቸው ሴቶች ጋር ተኝተሀል ..እና ከእኔ ጋር በምታደርገው ነገር ቅር መሰኘትህ አይቀርም ፣ ››ብላ ጨረሰች ።ሙሉ በሙሉ ተሸነፈች።
‹‹ ውዴ ፣ ስለ እንደዛ አይነት ነገር ፈፅሞ መጨነቅ አያስፈልግሽም -ሁሉን ነገር አብረን በዝግታና በትግስት እናደርገዋለን….እኔ አንቺን ከማንም ጋር ላወዳድርሽ ሀሳብ የለኝም….›› የእሱ አጽናኝና አበረታች ቃላት ጉዳቷን እና ውርደቷን ትንሽ አጠበላት።ንግግሩን ቀጠለ‹‹ይህ ፈተና አይደለም.›› ጎተተና ወደውስጥ ስቦ አስገባት፡፡ከዛ ቀስ አለና ቲሸርቷን ወደላይ ስቦ አወለቀውና ወደወለሉ ወረወረው….ከዛ ወደኋላ አጋዳማትና ደረቱ ላይ አስተኛት፡፡
‹‹እንግዲህ እጅ ሰጥቻለው…ችግር የለውም ካልክ….እንደፈለክ አድርገኝ››በማለት ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠቷን በይፋ አወጀች፡፡
‹‹ ውዴ አፈጻጸም ላይ ጭንቀት ካለብሽ ለምንድነው ለተወሰነ ጊዜ ሂደቱን የማትመሪው?››የሚል አስገራሚ ሀሳብ አቀረበላት፡፡
በድንገት መተንፈስ አቃታት።
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ..?ጭራሽ መምራት…‹‹በል የምታደርገውን እንደፈለግክ አድርግ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ደግሞ እኔም አንቺ የምታስቢውን ያህል ጎበዝ ላልሆን እችላለው ›› ብሎ ቀጠለ፣ በብልህ ጣቶቹን ጡቷቿን እያፍተለተለ ነው፡ ፡ቃተተች፡፡እሱ ሹክሹክታ በመሰለ ድምፅ መናገሩን ቀጠለ፡፡
ተንቀጠቀጠች፡፡ከአንገቷ ጀምሮ ወደታች ይልሳት ጀመር …ሳታስበው ሰውነቱ ላይ ተጣበቀችበት….ከታች እንትኑ ክፉኛ ቆረቆራት..ደስ የሚል መቆርቆር….የሚበላ እና ሚያሳክክ አይነት መቆርቆር …እሱም እንደተመቻት ስለገባው ይሰመስላል… በጠንካራ ጡንቻው ሰቅስቆ ወደራሱ አጥብቆ መሳሙን ቀጠለ….እያንዳንዷ የሚስማት ቦታ ልዩ አይነት የተለያየ ጣእም ያለው መስሎ ተሰማት…..ለዘመናት እንደዛ እየሳማት እንዲቆይ ተመኘች….እየቀለጠች ነው….ሆዷና ጀርባዋ በላብ እየታጠበ ነው፡፡እጁን ወደታች ሰደደና በለበሰችው ቁምጣዋንና ፓንቷን ሰቅስቆ ገባ……..‹‹ወይኔ ጉዴ ምን ሊያደርግ ነው?››አሰበች …የእጁን መዳፍ ብልቷ ላይ አሳረፈ……ድምፅ አውጥታ ማቃሰት ጀመረች….ከላዮ ላይ ተነሳና ቀና ብሎ የለበሰችውን ቁምጣን ፓንቷን አንድ ላይ ይዞ ወደታች ጎትቷ ማውለቅ ጀመረ…እግሯን ወደላይ ከፍ በማድረግ ተባበረችው፡፡ወደ ሰውነቱ አጥብቆ አቀፋትና ከጆሮዋ አንስቶ አንገቷን መሳም ጀመረ….ተቁነጠነጠች፡፡ቀስ እያለ መሳሙንም መዳበሱንም ሳያቋርጥ ወደታች ሄደ… ከዛ አንገቱን እግሯቾ መካከል ደፈቀ….ለፈለፈች….በመላ ሰውነቷ ቤንዚል ተርከፍክፎ ክብሪት የተጫራባት ነው የመሰላት…እጆቾን ፀጉሩ ላይ አድርጋ ታሻሸው ጀመር…ቀስ አለና እየሳማት ወደላይ መጓዝ ጀመረ… ከንፈሯ ጋር ሲደርስ ቀድማ ተጣበቀችበት….ሙሉ በሙሉ እግሮቾን መካከል ገብቷ ተዋሀዳት….ልዩ ጣፋጭነት ያለው ስቃይ ተሰማት…ስቃዩ እንዲያቆም ግን ፈፅሞ አትፈልግም…ይበልጥ መቃተት ይበልጥ መሰቃየት ፈልጋለች፡፡ሁለቱም እኩል ከፍተኛ ፍንዳታ ላይ ደረሱ አደኛው ሌለኛውን ወደራሳቸው ጨምቀው አቀፉ..ተርገፈገፉ…..በመከራ ተላቀቁና ጎን ለጎን ተዘረሩ፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ወደእሷ ዞረና‹‹እንዴት ነው?›› ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አረ…እንዲህ አይነት ጉብዝና መኖሩን እራሱ የት አውቃለው?››አለችው፡፡
ግንባሩን ወደ እርስዋ አስጠጋ ፣በረጅሙ ተነፈሰች።‹‹የእኔ ቆንጆ ሁለነገርሽ እንደሚያምር ታውቂያለሽ አይደል?...አይዞሽ ሁሉ ነገር ልዩ ይሆናል…ወደፊት ብዙ የምትማሪው ነገር ሊኖር ይችላል›› አላት፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይ በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ ጠረን ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡
…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።
ዛሬ አዲስአለም እና ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡
አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡
ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡
መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/
አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/
ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል
ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››
የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››
ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው መጡበት፡፡
ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››
‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››
‹‹እሺ አናግረኝ…
‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››
‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››
‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››
‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡
‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››
‹‹ጓደኛሽ?››
‹‹ማ ፀዲ››
‹‹አዎ…››
‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››
‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››
‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››
‹‹ወደእናቷ ጋር፡››
‹‹በይ እንቺ ደውይላት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይ በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ ጠረን ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡
…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።
ዛሬ አዲስአለም እና ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡
አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡
ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡
መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/
አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/
ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል
ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››
የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››
ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው መጡበት፡፡
ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››
‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››
‹‹እሺ አናግረኝ…
‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››
‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››
‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››
‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡
‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››
‹‹ጓደኛሽ?››
‹‹ማ ፀዲ››
‹‹አዎ…››
‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››
‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››
‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››
‹‹ወደእናቷ ጋር፡››
‹‹በይ እንቺ ደውይላት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ሚካኤል ከኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች ከፍተኛ ኃላፊ ጋር ሚስጥራዊ ስብስባ እያደረገ ነው፡፡እኚን ባለስልጣን ለማግኘትና ለማናገር በጣም ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፏል …በጣም ብዙ ገንዘብም ከስክሷል፡፡
‹‹እሺ አቶ ሚካኤል እንዳገኝህ ያሳመነን ወዳጄ ትልቅ ባለውለታዬ ነው ..ምን እንዳደርግልህ ነው የምትፈልገው?፡፡››ሲል ቦርጫቸውን እሻሹ ጠየቁት፡፡
‹‹ያው ጫፉን ያውቁታል ስለአባቴ ጉዳይ ነው››
‹‹እሱን ሰምቼለው…አባትህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሰው ነው፡፡ምን እንድረዳህ እንደፈለክም ያልገባኝ ለዛ ነው፡፡ታውቃለህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ፍርደኛ ቀጥታ ፋይሉ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ጋር ነው ሚላከው..እሳቸው ሲፈርሙበት የሞት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል…እስከዛው በእስር ይቆያል…ማንም ሰው ምንም ማድረግ አይችልም፡፡››
‹‹አውቃለው…..የእኔ ፍላጎት የሞት ፍርድ ተፈፃሚ እስኪሆንበት ያለው የማረሚያ ቤቱ አያያዝ እንዲሻሻልለት ለመጠየቅ ነው፡፡››
‹‹አዎ አንተን ለማግኘት ከመምጣቴ በፊት ስለአባትህ አጠቃላይ ሁኔታ በመጠኑ ለማጣራት ሞክሬ ነበር፡፡አሁን የታሰረው ጥብቅ በሆነ ጥበቃ ለብቻው መሆኑን ገልፀውልኛል፡፡››አሉን ፊትለፊታቸው የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ አንስተው ተጎነጩና መልሰው አስቀመጡት፡፡
ሚካኤልም ‹‹አዎ ያስጨነቀኝ እኮ ያ ነው፡፡››ሲል መለሰላቸው፡፡
‹‹ያ ለምን እንደሆነ መቼስ ታውቃለህ፡፡አባትህ ከሌሎች በእስር ቤት ካሉ ታራሚሆች ጋር በማሰር ከማረሚያ ቤቱ ለማምለጥ ሞክሮ አንድ የፖሊስ አባልና ሁለት እስረኛ ሞተዋል፡፡የዛ ኦፕሬሽን ዋናው ማስተር ማይንድ እና መሪ ደግሞ አባትህ ነበር…ያ ውሳኔ የተወሰነበት ከዛ ክስተት በኋላ ነው፡፡ለፖሊስ መገደል ምክንያት መሆን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መገመት አይከብድህም››
‹‹አዎ አውቃለው…ግን እኮ በጣም ተቀጣ..እዛ ጨለማ ክፍል በሰንሰለት ተጠፍሮ መኖር ከጀመረ ስድስት ወር አለፈው፡፡እሺ ብቻውን ይታሰር….ቢያንስ ከጨለማ ክፍል የሚወጣበትና ከሰንሰለት እስርም የሚገላገልበት እድል ቢኖር፡፡ዋናው ከሰው እንዳይቀላቀልና ተመሳሳይ አይነት የማምለጥ ሙከራ እንዳይሞክር አይደል››ሲል በንግግሩ ቃናም በአይኖቹም ተማፀናቸው፡፡
‹‹ይመስለኛል ..ያም ብቻ አይደለም..በእሱ ምክንያት የሞተው ፖሊስ በወህኒ ቤት ውስጥ በፖሊስችም ሆነ በእስረኞች በጣም ተወዳጅ ስለነበረ….በጓደኞቹ ዘንድ ከፍተኛ ብስጭት ፈጥሯል….እና አንድም በጣም እንዲቀጣ ይፈልጋሉ በሌላ ጎኑም በተግባሩ በተበሳጩ ሰዎች ጥቃት እንዳይደርስበትም ስጋት ስላለ መጠበቅ ይፈልጋሉ፡፡››
‹‹‹አውቃለሁ…ያ ጉዳይ በመፈፀሙ እኔም ከፍተኛ ልብ ስብራት ደርሶብኛል ፣ የሞች ፖሊስ ቤተሰቦች አግኝቼ ለማነጋገር ሞክሬለው፡፡ባለቤቱንና አንድ ልጁን ወዲው ነበር ያገኘዋቸው….እና ምንም እንኳን እሱን መልሼ ላመጣላቸው ባልችልም በኑሮ ግን እንዳይቸገሩ የተቻለኝን እያደረኩ ነው፡፡ለሚስቱ ስራ እንድታገኝ አድርጌለው….የልጁንም ትምህርት ቤት ክፍያ እና አንዳንድ ወጪዎች እየከፈልኩ ነው….ምንም ሆነ ምንም ወደፊትም ያንን ማድረጌን አላቋርጥም፣እባኮት እርሶ በተቻሎት መጠን ይርዱኝ…ምንም አይነት ቤተሰብ እንዳይጠይቀውም ስለተከለከለ እኔ እንኳን ካየሁት ስድስት ወር አልፎኛል…››
‹‹በእውነት እያደረከው ስላለ ነገር ምስጋና ይገባሀል..ትልቅ ሰው ነህ!!እንግዲህ እንዲህ እናድርግ….አንድ አስር ቀን ስጠኝ እና ሁኔታውን በተሻለ ሁኔታ ላጥና..ከዛ ሌሎች ጓደኞቼንም ቢሆን አስቸግሬ ማድረግ የምችለውን ነገር ላስብበትና መልሰን እናውራበት››
‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው…..ምን አልባት ጓደኞቾትን ሲያስቸግሩ የሚያስፈልግ ነገር ካለ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አሟላለሁ…፡፡››ሲል ቃል ገባ፡፡
‹‹ችግር የለም… የሚስፈልግ ነገር ካለ አሳውቅሀለው….እነደነገርኩህ አንተን እንድረዳህ የጠየቀኝ ሰው በጣም ወዳጄና ባለውለታዬ ነው…..እና በእኔ አቅም ማድረግ የምችለውን ነገር ሁሉ እንደማደርግና የአባትህን በእስር ቤት ውስጥ ያለውን አያያዝ ለማሻሻል ጥረት እንደማደረግ ልገልጽልህ አፈልጋለው…በተለይ አባትህን የመጠየቅ መብትህን መልሰህ እንድታገኝ ማድረግ ምችል ይመስለኛል፡፡››
‹‹አመሰግናለው..ስልኮትን በጉጉት ጠብቃለው፡፡›› በዛው ተለያዩ
////
ፀአዳ በአራተኛው ቀን ስሜቷን አብርዳ….መረበሿን አረጋግታ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ከዶዶላ ተመልሳ አዳማ እስክትገባ ስልኳን አልከፈተችም ነበር፡፡ቤቷ ደርሳ አረፍ እንዳለች ከፈተችና ለአዲስ አለም ደወለችላት፡፡
አዲስአለም ከሰላምታ ሳይሆን ከስድብ ነው የጀመረችው‹‹አንቺ ቅሌታም…..ጤነኛ ነሽ ግን?››
‹‹ቀስ …ይሄ ሁሉ ቁጣ ናፍቆት ነው ወይስ ሌላ ምክያት አለው?፡፡››
በስድቧ ገፋችበት ‹‹ወሬኛ ነሽ እሺ…..ለመሆኑ አሁን የት ነሽ?››
‹‹ቤቴ ነኛ››
‹‹ማለት እዚህ አዳማ?››
‹‹አዎ..ምነው ሌላ ቦታ ቤት አለኝ እንዴ?››
‹‹እኔ ምን አውቅልሻለው….ግን ሳስበው በቅርብ አዲስአበባ ላይ ቤት የሚኖርሽ ይመስለኛል….በቃ ጠብቂኝ አሁኑኑ መጣሁ…፡፡››
‹‹ኸረ እኔ ራሴ መጣለሁ…፡፡››
‹‹መጣው እኮ አልኩሽ፡፡››ስልኩን ጠረቀመችባት፡፡
‹‹ዛሬ ልትደበድበኝ ሁሉ ትችላለች››ስትል አሰበችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ማስተካከል ጀመረች ..ተዘግቶ ስለከረመ እምክ እምክ ይላል…መስኮቱን ከፋፈተች…ሰንደል ለኮሶችና በየኮርነሩ ላይ ሰካካች… ቡና ለማፍላት ሲኔ ደረደረች፣ከሰል በማቀጣጠል ላይ እያለች አዲስ አለም መጣች፡፡
ጠየቀቻት ካሰበችው ጊዜ በጣም ፈጥና በመምጠቷ ተገርማ‹‹እንዴ ..!!ስትደውይልኝ መንገድ ላይ ነበርሽ እንዴ?››ስትል ….፡፡
ልትስማት ስትጠጋት ወደኃ ሸሸቻትና ገፍትራት ወደቤት ገባች….ፀአዳማ እያቀጣጠለች የነበረውን ከሰል ትታ ከኃላ ተከተለቻት፡፡
‹‹ምስር የታለች?››
‹‹ጎረቤት ልትጫወት ሄዳለች››
‹‹ቆይ አንቺ ግን ያምሻል..?እንዴት አንድ ነር ሳትነግሪኝ ብን ብለሽ ትሔጃለሽ…እሺ መሄዱንስ ሂጂ እንዴትሰ ስልክሽን ትዘጊያለሽ?››
‹‹ስልኬ እኮ ተበላቶብኝ ነው››
‹‹አረ ባክሽ..አሁን እኔን የምትሸውጂኝ ይመስልሻል?››
‹‹‹እሺ በቃ ማንንም ለማውራት ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም…በፀጥታ ማሰብ ነበር የፈለኩት..በዛ ላይ አንቺ የሰርግና የመልስ ግርግር ላይ ስለሆንሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም››
‹‹ወይ ረበሺኝ እኮ..እኔን ብቻ ሳይሆን ባሌንም ጭምር ነው በደንብ የረበሺን፡፡››
‹‹እንግዲህ አዝናለው…..በጣም ይቅርታ›
‹‹ደግሞ ሰውዬሽ..አብዶልሻል….››
‹‹የቱ ሰውዬ?››ግራ በመጋባት ጠየቀች፡፡
‹‹ስንት ሰውዬ ነው ያለሽ…?ዘሚካኤል ነዋ..ከደበቅሺበት ውለጂያት ብሎ ሊያንቀኝ››
‹‹እንዴ ደወለልሽ እንዴ?››
ምን ይደውልልኛል…በዛን ቀን ልክ ያንቺ መልእክት ደርሶኝ እሱን ከሚካኤል ጋር አንብበን እየተገረምን ሳለ ቤት ድረስ መኪናውን እያከነፈ መጣና ሰፈሩን በመኪናው ክላክስ አደበላለቀው…ምን ሆኖ ነው ብዬ ስወጣ መኪና ውስጥ አስገባኝና ከሰፈር ይዞኝ ሄደ….››ብላ የዛን ቀን የሆነውን በዝርዝር ተረከችላት፡፡›
ፀአዳ በሰማችው ነገር በጣም ተገረመች‹‹ፈፅሞ እንደዛ ያደርጋል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር…ግፋ ቢል ደውሎ የሆነ ነገር ይልሻል ብዬ ነው ያሰብኩት፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?ልጁ እኮ ጨርቁን ጥሎልሻል››
‹‹ማለት?››
‹‹አፍቅሯሻል እያልኩሽ ነው››
‹‹እኔ ፍቅር አልፈልግም››
‹‹እና ወሲብ ነው ምትፈልጊው?
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ሚካኤል ከኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች ከፍተኛ ኃላፊ ጋር ሚስጥራዊ ስብስባ እያደረገ ነው፡፡እኚን ባለስልጣን ለማግኘትና ለማናገር በጣም ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፏል …በጣም ብዙ ገንዘብም ከስክሷል፡፡
‹‹እሺ አቶ ሚካኤል እንዳገኝህ ያሳመነን ወዳጄ ትልቅ ባለውለታዬ ነው ..ምን እንዳደርግልህ ነው የምትፈልገው?፡፡››ሲል ቦርጫቸውን እሻሹ ጠየቁት፡፡
‹‹ያው ጫፉን ያውቁታል ስለአባቴ ጉዳይ ነው››
‹‹እሱን ሰምቼለው…አባትህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሰው ነው፡፡ምን እንድረዳህ እንደፈለክም ያልገባኝ ለዛ ነው፡፡ታውቃለህ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ፍርደኛ ቀጥታ ፋይሉ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ጋር ነው ሚላከው..እሳቸው ሲፈርሙበት የሞት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል…እስከዛው በእስር ይቆያል…ማንም ሰው ምንም ማድረግ አይችልም፡፡››
‹‹አውቃለው…..የእኔ ፍላጎት የሞት ፍርድ ተፈፃሚ እስኪሆንበት ያለው የማረሚያ ቤቱ አያያዝ እንዲሻሻልለት ለመጠየቅ ነው፡፡››
‹‹አዎ አንተን ለማግኘት ከመምጣቴ በፊት ስለአባትህ አጠቃላይ ሁኔታ በመጠኑ ለማጣራት ሞክሬ ነበር፡፡አሁን የታሰረው ጥብቅ በሆነ ጥበቃ ለብቻው መሆኑን ገልፀውልኛል፡፡››አሉን ፊትለፊታቸው የተቀመጠውን የውስኪ ብርጭቆ አንስተው ተጎነጩና መልሰው አስቀመጡት፡፡
ሚካኤልም ‹‹አዎ ያስጨነቀኝ እኮ ያ ነው፡፡››ሲል መለሰላቸው፡፡
‹‹ያ ለምን እንደሆነ መቼስ ታውቃለህ፡፡አባትህ ከሌሎች በእስር ቤት ካሉ ታራሚሆች ጋር በማሰር ከማረሚያ ቤቱ ለማምለጥ ሞክሮ አንድ የፖሊስ አባልና ሁለት እስረኛ ሞተዋል፡፡የዛ ኦፕሬሽን ዋናው ማስተር ማይንድ እና መሪ ደግሞ አባትህ ነበር…ያ ውሳኔ የተወሰነበት ከዛ ክስተት በኋላ ነው፡፡ለፖሊስ መገደል ምክንያት መሆን ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መገመት አይከብድህም››
‹‹አዎ አውቃለው…ግን እኮ በጣም ተቀጣ..እዛ ጨለማ ክፍል በሰንሰለት ተጠፍሮ መኖር ከጀመረ ስድስት ወር አለፈው፡፡እሺ ብቻውን ይታሰር….ቢያንስ ከጨለማ ክፍል የሚወጣበትና ከሰንሰለት እስርም የሚገላገልበት እድል ቢኖር፡፡ዋናው ከሰው እንዳይቀላቀልና ተመሳሳይ አይነት የማምለጥ ሙከራ እንዳይሞክር አይደል››ሲል በንግግሩ ቃናም በአይኖቹም ተማፀናቸው፡፡
‹‹ይመስለኛል ..ያም ብቻ አይደለም..በእሱ ምክንያት የሞተው ፖሊስ በወህኒ ቤት ውስጥ በፖሊስችም ሆነ በእስረኞች በጣም ተወዳጅ ስለነበረ….በጓደኞቹ ዘንድ ከፍተኛ ብስጭት ፈጥሯል….እና አንድም በጣም እንዲቀጣ ይፈልጋሉ በሌላ ጎኑም በተግባሩ በተበሳጩ ሰዎች ጥቃት እንዳይደርስበትም ስጋት ስላለ መጠበቅ ይፈልጋሉ፡፡››
‹‹‹አውቃለሁ…ያ ጉዳይ በመፈፀሙ እኔም ከፍተኛ ልብ ስብራት ደርሶብኛል ፣ የሞች ፖሊስ ቤተሰቦች አግኝቼ ለማነጋገር ሞክሬለው፡፡ባለቤቱንና አንድ ልጁን ወዲው ነበር ያገኘዋቸው….እና ምንም እንኳን እሱን መልሼ ላመጣላቸው ባልችልም በኑሮ ግን እንዳይቸገሩ የተቻለኝን እያደረኩ ነው፡፡ለሚስቱ ስራ እንድታገኝ አድርጌለው….የልጁንም ትምህርት ቤት ክፍያ እና አንዳንድ ወጪዎች እየከፈልኩ ነው….ምንም ሆነ ምንም ወደፊትም ያንን ማድረጌን አላቋርጥም፣እባኮት እርሶ በተቻሎት መጠን ይርዱኝ…ምንም አይነት ቤተሰብ እንዳይጠይቀውም ስለተከለከለ እኔ እንኳን ካየሁት ስድስት ወር አልፎኛል…››
‹‹በእውነት እያደረከው ስላለ ነገር ምስጋና ይገባሀል..ትልቅ ሰው ነህ!!እንግዲህ እንዲህ እናድርግ….አንድ አስር ቀን ስጠኝ እና ሁኔታውን በተሻለ ሁኔታ ላጥና..ከዛ ሌሎች ጓደኞቼንም ቢሆን አስቸግሬ ማድረግ የምችለውን ነገር ላስብበትና መልሰን እናውራበት››
‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው…..ምን አልባት ጓደኞቾትን ሲያስቸግሩ የሚያስፈልግ ነገር ካለ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ አሟላለሁ…፡፡››ሲል ቃል ገባ፡፡
‹‹ችግር የለም… የሚስፈልግ ነገር ካለ አሳውቅሀለው….እነደነገርኩህ አንተን እንድረዳህ የጠየቀኝ ሰው በጣም ወዳጄና ባለውለታዬ ነው…..እና በእኔ አቅም ማድረግ የምችለውን ነገር ሁሉ እንደማደርግና የአባትህን በእስር ቤት ውስጥ ያለውን አያያዝ ለማሻሻል ጥረት እንደማደረግ ልገልጽልህ አፈልጋለው…በተለይ አባትህን የመጠየቅ መብትህን መልሰህ እንድታገኝ ማድረግ ምችል ይመስለኛል፡፡››
‹‹አመሰግናለው..ስልኮትን በጉጉት ጠብቃለው፡፡›› በዛው ተለያዩ
////
ፀአዳ በአራተኛው ቀን ስሜቷን አብርዳ….መረበሿን አረጋግታ ልጇን ይዛ መጣች፡፡ከዶዶላ ተመልሳ አዳማ እስክትገባ ስልኳን አልከፈተችም ነበር፡፡ቤቷ ደርሳ አረፍ እንዳለች ከፈተችና ለአዲስ አለም ደወለችላት፡፡
አዲስአለም ከሰላምታ ሳይሆን ከስድብ ነው የጀመረችው‹‹አንቺ ቅሌታም…..ጤነኛ ነሽ ግን?››
‹‹ቀስ …ይሄ ሁሉ ቁጣ ናፍቆት ነው ወይስ ሌላ ምክያት አለው?፡፡››
በስድቧ ገፋችበት ‹‹ወሬኛ ነሽ እሺ…..ለመሆኑ አሁን የት ነሽ?››
‹‹ቤቴ ነኛ››
‹‹ማለት እዚህ አዳማ?››
‹‹አዎ..ምነው ሌላ ቦታ ቤት አለኝ እንዴ?››
‹‹እኔ ምን አውቅልሻለው….ግን ሳስበው በቅርብ አዲስአበባ ላይ ቤት የሚኖርሽ ይመስለኛል….በቃ ጠብቂኝ አሁኑኑ መጣሁ…፡፡››
‹‹ኸረ እኔ ራሴ መጣለሁ…፡፡››
‹‹መጣው እኮ አልኩሽ፡፡››ስልኩን ጠረቀመችባት፡፡
‹‹ዛሬ ልትደበድበኝ ሁሉ ትችላለች››ስትል አሰበችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ቤቱን ማስተካከል ጀመረች ..ተዘግቶ ስለከረመ እምክ እምክ ይላል…መስኮቱን ከፋፈተች…ሰንደል ለኮሶችና በየኮርነሩ ላይ ሰካካች… ቡና ለማፍላት ሲኔ ደረደረች፣ከሰል በማቀጣጠል ላይ እያለች አዲስ አለም መጣች፡፡
ጠየቀቻት ካሰበችው ጊዜ በጣም ፈጥና በመምጠቷ ተገርማ‹‹እንዴ ..!!ስትደውይልኝ መንገድ ላይ ነበርሽ እንዴ?››ስትል ….፡፡
ልትስማት ስትጠጋት ወደኃ ሸሸቻትና ገፍትራት ወደቤት ገባች….ፀአዳማ እያቀጣጠለች የነበረውን ከሰል ትታ ከኃላ ተከተለቻት፡፡
‹‹ምስር የታለች?››
‹‹ጎረቤት ልትጫወት ሄዳለች››
‹‹ቆይ አንቺ ግን ያምሻል..?እንዴት አንድ ነር ሳትነግሪኝ ብን ብለሽ ትሔጃለሽ…እሺ መሄዱንስ ሂጂ እንዴትሰ ስልክሽን ትዘጊያለሽ?››
‹‹ስልኬ እኮ ተበላቶብኝ ነው››
‹‹አረ ባክሽ..አሁን እኔን የምትሸውጂኝ ይመስልሻል?››
‹‹‹እሺ በቃ ማንንም ለማውራት ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም…በፀጥታ ማሰብ ነበር የፈለኩት..በዛ ላይ አንቺ የሰርግና የመልስ ግርግር ላይ ስለሆንሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም››
‹‹ወይ ረበሺኝ እኮ..እኔን ብቻ ሳይሆን ባሌንም ጭምር ነው በደንብ የረበሺን፡፡››
‹‹እንግዲህ አዝናለው…..በጣም ይቅርታ›
‹‹ደግሞ ሰውዬሽ..አብዶልሻል….››
‹‹የቱ ሰውዬ?››ግራ በመጋባት ጠየቀች፡፡
‹‹ስንት ሰውዬ ነው ያለሽ…?ዘሚካኤል ነዋ..ከደበቅሺበት ውለጂያት ብሎ ሊያንቀኝ››
‹‹እንዴ ደወለልሽ እንዴ?››
ምን ይደውልልኛል…በዛን ቀን ልክ ያንቺ መልእክት ደርሶኝ እሱን ከሚካኤል ጋር አንብበን እየተገረምን ሳለ ቤት ድረስ መኪናውን እያከነፈ መጣና ሰፈሩን በመኪናው ክላክስ አደበላለቀው…ምን ሆኖ ነው ብዬ ስወጣ መኪና ውስጥ አስገባኝና ከሰፈር ይዞኝ ሄደ….››ብላ የዛን ቀን የሆነውን በዝርዝር ተረከችላት፡፡›
ፀአዳ በሰማችው ነገር በጣም ተገረመች‹‹ፈፅሞ እንደዛ ያደርጋል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር…ግፋ ቢል ደውሎ የሆነ ነገር ይልሻል ብዬ ነው ያሰብኩት፡፡››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..?ልጁ እኮ ጨርቁን ጥሎልሻል››
‹‹ማለት?››
‹‹አፍቅሯሻል እያልኩሽ ነው››
‹‹እኔ ፍቅር አልፈልግም››
‹‹እና ወሲብ ነው ምትፈልጊው?
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከአስር ቀን በኃላ ያሉት ባለስልጣን ከሳምንት በኃላ ደወሉለት..አልጠበቀው ነበር፡፡‹‹ሚካኤል አንድ ጥሩ ዜና አለኝ››
‹‹ምንድነው ጌታዬ?››በጉጉት ጠየቀ፡፡
‹‹ነገ ሰባት ሰዓት ላይ አባትህን እንድታገኝ ከእስርቤቱ አስተዳዳሪ ፍቃድ አግንቼልሀለው፡፡››
‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው›..እግዜር ይስጥልኝ››
‹‹አዎ በሰአቱ ሂድና…ቀጥታ አሁን በምልክልህ ስልክ እዛ እንደደረስ ደውልለት… አስተዳዳሪው ራሱ ይቀበልህና ሚሆነውን ያደርጋል….ሌሎች ነገሮችን እየሰራሁባቸው ነው….እስከዛው በዚህ ተፅናና…››
‹‹እሺ ጌታ ..በጣም ነው የማመሰግነው››
ስልኩን ዘጋና በደስታ ዘለለ…ልጇን እያጠባች ሁኔታውን ስትከታተል የነበረችው አዲስአለም ..‹‹ምን ተገኘ..ሎቶሪ ወጣልህ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹በይው…ነገ አባዬን እንድጠይቀው ተፈቀደልኝ››
‹‹በእውነት..በጣም ደስ ይላል››
‹‹አዎ….ምንድነው ይዤለት የምሄደው…..?››ሲል ከፈንጠዝያው ሳይወጣ ጠየቀ፡፡
‹‹አንተ ምን አልባት ቅያሪ ልብስ የላቸውም ይሆናል..ልብስ ምናም አዘጋጅ..እኔ ደግሞ የሚበላ ነገር አዘጋጃለው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ ..የእኔ ማር በጣም ደስ ብሎኛል….››
‹‹ደስ ይላል..ግን ያው አባትህ እስር ቤት ከገቡ ጀምሮ ልትጠይቃቸው በሄድክ ቁጥር በምን አይነት አቀባበል እንደሚቀበሉህ ታውቃለህ…እንዲህ በመፈንጠዝ ሄደህ በኃላ አላናገረኝም….መጥተህ አትጠይቀኝ አለኝ…ምናምን ብለህ እንዳትበሳጭ››ስትል ስጋቷን ገለፀችለት፡፡
‹‹አረ…የፈለገ ይበል እኔ አይኑን ማየት ብቻ ነው የምፈልገው….ከፈለገ ለምን ልትጠይቀኝ መጣህ ብሎ በቡጢ አይነርተኝም ..ግድ አይሰጠኝም››
አሳዘናት…‹‹ሁሉም ሰው ምናለ እንዳአንተ ሰው ወዳጅና ሌላውን የሚረዳ ቢሆን››ስትል በውስጦ አሰበች‹አይ እንደዛ ከተዘጋጀህ ጥሩ››አለችው፡፡
‹‹በቃ ወጣው ….በዛው ለአባዬ የሚሆን ልብስ ገዛዛለሁ››ብሎ ሚስቱን ጉንጯን ልጁን ግንባሩን ሳመና ወጥቶ ሄደ፡፡
ሚካኤል ለአባቱ ልብስና የሚበሉ የተለያዩ ትኩስ ምግቦችን ተሸክሞ ልክ በተባለው ሰዓት ወህኒ ቤት ጊቢ ደርሶ ስልኩን ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ኩማንደር …ሚካኤል ነኝ…ቀጠሮ ነበረኝ፡፡››
‹‹እ ሚካኤል ….ጥበቃ ላይ ካሉት ፖሊሶች አስርሀለቃ ላቀው በልና ንገረው …ነግሪዋለው ወደእኔ ይዞህ ይመጣል፡፡››የሚል አስደሳች መልስ አገኘ፡፡
‹‹እሺ ኩማንደር አመሰግናለው››
ስልኩን ዘጋና ፊት ለፊቱ ያለውን ፖሊስ ‹አስር ሀለቃ ላቀውን› እንዲያሳየው ጠየቀው….እዛው በቅርብ የነበረ ፖሊስ ጠቆመው፡፡ማንነቱን ለፖሊሱ ነገረና ..ለአባቱ ይዞ የመጣውን እቃ እንዲያስረክ ካደረገ በኃላ ቀጥታ ወደኮማንደር ቢሮ ይዞት ሄዳ፡፡ፖሊሱ ክፉሉን ቆርቆሮ ከፍቶ አስገባውና መልሶ ሄደ፡፡
ሲገባ የገጠመው ግዙፍና ግርማ ሞገስ ያለው ቢሮ ነው፡፡እዚህ ቀፋፊ ወህኒ ቤት ውስጥ እንዲህ አይነት የሚያምር ቢሮ ይኖራል ብሎ ገምቶ አያውቅም፡፡ፀጉራቸው ሙሉ በሙሉ ቀለሙን ቀይሮ ነጭ የሆነው ግዙፉ ጠይም ቆፍታምና ሰው ከግዙፉ ጠረጴዛ ኃላ ባለ የቆዳ ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጠው ይታያሉ….በጎርናና እና ሻካራ ድምጻቸው ‹‹ግባ አቶ ሚካኤል…..››አሉት
ሄደና ወደእሳቸው ቀርቦ ለሰላምታ እጁን ዘረጋላቸው…በመጠኑ ከመቀመጫቸው እንደመነሳት አሉና እጃቸውን ዘርግተው ጨበጡትና‹‹ተቀመጥ አቶ ሚካኤል›
እሺ ብሎ አንዱን ወንበር ሳበና ተቀመጠ‹‹ኩማንደር ስለአስቸገርኩት ይቅርታ….ያው የቤተሰብ ጉዳይ ስለሆነብኝ ነው››ሲል ተናገረ፡፡
‹‹ይገባኛል…እንደውም ጥሩ ልጅ ስለሆንክ መመስገን አለብህ…መቼስ ማረሚያ ቤታችን በአባትህ ላይ የወሰደው አቋም ለምን እንደሆነ ይገባሀል አይደል?አዎ ይገባሀል እንጂ …በእኛ ልትበሳጭ ፍፅም አትችልም፡፡››
‹‹አዎ በትክክል ይገባኛል….››ሲል በአጭሩ መለሰ፡፡
‹‹አሁን ያው ከአንተ ጋር እየተነጋገርን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን ሁኔታዎችን ለማስተካከል እንሞክራለን….ዋናው አንተ አባትህንን ምን ያህል ?ማገዝ ትፈልገለህ የሚለው ነው››አሉና ፈገግ ብለው በሲጋራ የበለዘ ጥርሳቸውን አሳዩት፡፡
‹‹ኮማንደር አባቴ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት መሞቻ ቀኑን የሚጠብቅ ሰው ነው…እና ያ ቀን አስኪደርስ ድረስ በተቻለ መጠን በተመቻቸ ሁኔታ እንዲያሳልፍ ማንኛውንም ነገር ለማድረግ ፍቃደኛ ነኝ፡፡አባቴ ይሄንን ቀፋፊ ወንጀል ሰርቶ ወህኒ ቤት ከመግቱ በፊት ለቤተቡ አይደለም ቸገረኝ ላለ ሰው ሁሉ ልብ የሚያዝንና እጁ የሚፈታ መልካምና የተከበረ ሰው ነበር…..ምንም ሆነ ምንም ፍፃሚዊ እንዲህ አሳዛኝ መሆን የለበትም፡፡
‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ ማድረግ ይምንችለውን ሁሉ እናያለን፡፡››አሉን ወደፊት ተንጠራርተው መጥሪያውን ተጫኑ..አንድ ፖሊስ መጣና ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠ…‹‹ሳጂን ታራሚ ቅጣውን እዚህ አስመጣልን››ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡ
ፖሊሱ ትዕዛዙን ተቀበለና ተመልሶ ወጥቶ ሄደ….ከ5 ደቂቃ በኃላ እስከአሁን ያለሳተዋለው በኩማንደሩ መቀመጫ በቀኝ በኩል የምትገኝ ጠበብ የጀርባ በራፍ ተቆረቀረ…ኮማንደሩ ዝርጥት ሰውነታቸው እየከበዳቸው በመከራ ተነሱና በራፉ ከውስጥ ከፍተው ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ አይኖቹን የተከፈተው በራፍ ላይ እንደተከለ መጠበቅ ጀመረ…ሰው ከማየቱበፊት ብረት ቅጭልጭልታ በጇሮው ሞላ..…ከዛ በተቀመጠበት ደንዝዞ ቀረ..አባቱን ከስድስት ወራት በፊት ነው ያየው…ሰው በስድስት ወር በዚህ መጠና ሊቀየር እንደሚችል ግምቱ የለውም ፡ፀጉሩ ተንጨፍርሮ ተንጨፍርሮ ጉድሮ ሆኖ ግንባሩ ላይ ተደፍቷል…ፂሙ አድጎ ግማሽ ፊቱን ሸፍኖት ያረጀ አንበሳ አስመስሎታል…ከመክሳቱ የተነሳ ሁለቱ ጉንጮቹ አንድ ላይ የተጣበቁ ይመስላል፡፡አይኖቹ ጥልቅ ጉድጓዱ ውስጥ ያሉ ደማቅ አንፖሎች ነው የሚመስሉት…ሚካኤል እንባው ዝርግፍ አለ..ኮማደሩ ከተቀመጡበት ተነሱና ..ለብቻችሁ ጊዜ ልስጣችሁ..አንድሰዓት አላችሁ……በፊት ለፊተኛው በራፍ ክፉሉን ለቀውላቸው ወጡና ከውጭ ቀርቅረውባቸው ብቻቸውን ተዋቸው…
እንደምንም እራሱን አበረታቶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደአባቱ ሄደ…ልጅ እያለ ባለግርማ ሞገሳሙ አባቱ ወደ ቤት መምጣቱን የሚያውቀው የመኪናውን ክላክስ ሲሰማ ነበር..ካዛ ከወንድሙ ጋር ሮጠው ከቤት ይወጡና ወደእሱ ይንደረደራሉ…ከዛ ለልጆቹ የገዛላቸውን ፍራፍሬ ወይም ሌሎች ጣፍጭ ነገሮች የያዘ ፔስታል ይዞ ከመኪናው ሲወርድ እሱን ጨምሮ ሶስቱም ልጆቹ በሽሚያ አንዱ ቀኝ እግሩን ሌላው ግራ እሩን ያቅፍትና በልዩ ፈንጠዝያ ይቀበሉታል…እሱም ስራቸው ይንበረከክና አንዱን ጉንጩን ሌላዋን ግንባሩን እያሳመና እየዳበሰ ይዞቸው ወደቤት ይገባል…አባትዬው ለልጆቹ እንስፍስፍ የሚባል አባት ነበር..በተለይ ዬቱ ታላቅ የሆነችውን ሴት ልጁን በልዩነት ንው የሚወዳት…እሷም በአባቷ በምንም አይነት ሁኔታ የማትደራደር የእሱ ተመራጭ ልጅ ነበረች…እና እንደዛ ኩሩና ሽቅርቅር የነበረው አባቱ አሁን አፅሙ ብቻ ነው ያለው..ሄዶ በፍራቻ ተጠመጠመበት.. ጠረኑ ወደኃላ ይገፋተራል…አባትዬው ምንም አይነት ምላሽ አላሳየውም..እየጎተተ ወደወንበሮቹ ወሰደውና አስቀመጠውና ከፊት ለፊቱ ተቀመጠ፡፡
‹‹አባዬ እንዴት ነህ?››
ለእሱ መልስ ከመስጠት ይልቅ ‹‹ለምን እንደዚህ አደረክ?››ሲል አንቧረቀበት፡፡
‹‹ማለት? ምን አደረኩ?››ምን ስህተት እንደሰራ ባለማወቅ በፍራቻ ጠየቀ፡፡
‹‹ለምን አገኘኸኝ..?እንዴት እንደተቀጣሁና ምን አይነት ቀፋፊ አውሬ እንደሆንኩ ለማየት ነው የመጣኸው?››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከአስር ቀን በኃላ ያሉት ባለስልጣን ከሳምንት በኃላ ደወሉለት..አልጠበቀው ነበር፡፡‹‹ሚካኤል አንድ ጥሩ ዜና አለኝ››
‹‹ምንድነው ጌታዬ?››በጉጉት ጠየቀ፡፡
‹‹ነገ ሰባት ሰዓት ላይ አባትህን እንድታገኝ ከእስርቤቱ አስተዳዳሪ ፍቃድ አግንቼልሀለው፡፡››
‹‹በእውነት በጣም ነው የማመሰግነው›..እግዜር ይስጥልኝ››
‹‹አዎ በሰአቱ ሂድና…ቀጥታ አሁን በምልክልህ ስልክ እዛ እንደደረስ ደውልለት… አስተዳዳሪው ራሱ ይቀበልህና ሚሆነውን ያደርጋል….ሌሎች ነገሮችን እየሰራሁባቸው ነው….እስከዛው በዚህ ተፅናና…››
‹‹እሺ ጌታ ..በጣም ነው የማመሰግነው››
ስልኩን ዘጋና በደስታ ዘለለ…ልጇን እያጠባች ሁኔታውን ስትከታተል የነበረችው አዲስአለም ..‹‹ምን ተገኘ..ሎቶሪ ወጣልህ እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹በይው…ነገ አባዬን እንድጠይቀው ተፈቀደልኝ››
‹‹በእውነት..በጣም ደስ ይላል››
‹‹አዎ….ምንድነው ይዤለት የምሄደው…..?››ሲል ከፈንጠዝያው ሳይወጣ ጠየቀ፡፡
‹‹አንተ ምን አልባት ቅያሪ ልብስ የላቸውም ይሆናል..ልብስ ምናም አዘጋጅ..እኔ ደግሞ የሚበላ ነገር አዘጋጃለው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ ..የእኔ ማር በጣም ደስ ብሎኛል….››
‹‹ደስ ይላል..ግን ያው አባትህ እስር ቤት ከገቡ ጀምሮ ልትጠይቃቸው በሄድክ ቁጥር በምን አይነት አቀባበል እንደሚቀበሉህ ታውቃለህ…እንዲህ በመፈንጠዝ ሄደህ በኃላ አላናገረኝም….መጥተህ አትጠይቀኝ አለኝ…ምናምን ብለህ እንዳትበሳጭ››ስትል ስጋቷን ገለፀችለት፡፡
‹‹አረ…የፈለገ ይበል እኔ አይኑን ማየት ብቻ ነው የምፈልገው….ከፈለገ ለምን ልትጠይቀኝ መጣህ ብሎ በቡጢ አይነርተኝም ..ግድ አይሰጠኝም››
አሳዘናት…‹‹ሁሉም ሰው ምናለ እንዳአንተ ሰው ወዳጅና ሌላውን የሚረዳ ቢሆን››ስትል በውስጦ አሰበች‹አይ እንደዛ ከተዘጋጀህ ጥሩ››አለችው፡፡
‹‹በቃ ወጣው ….በዛው ለአባዬ የሚሆን ልብስ ገዛዛለሁ››ብሎ ሚስቱን ጉንጯን ልጁን ግንባሩን ሳመና ወጥቶ ሄደ፡፡
ሚካኤል ለአባቱ ልብስና የሚበሉ የተለያዩ ትኩስ ምግቦችን ተሸክሞ ልክ በተባለው ሰዓት ወህኒ ቤት ጊቢ ደርሶ ስልኩን ደወለ፡፡
‹‹ሄሎ ኩማንደር …ሚካኤል ነኝ…ቀጠሮ ነበረኝ፡፡››
‹‹እ ሚካኤል ….ጥበቃ ላይ ካሉት ፖሊሶች አስርሀለቃ ላቀው በልና ንገረው …ነግሪዋለው ወደእኔ ይዞህ ይመጣል፡፡››የሚል አስደሳች መልስ አገኘ፡፡
‹‹እሺ ኩማንደር አመሰግናለው››
ስልኩን ዘጋና ፊት ለፊቱ ያለውን ፖሊስ ‹አስር ሀለቃ ላቀውን› እንዲያሳየው ጠየቀው….እዛው በቅርብ የነበረ ፖሊስ ጠቆመው፡፡ማንነቱን ለፖሊሱ ነገረና ..ለአባቱ ይዞ የመጣውን እቃ እንዲያስረክ ካደረገ በኃላ ቀጥታ ወደኮማንደር ቢሮ ይዞት ሄዳ፡፡ፖሊሱ ክፉሉን ቆርቆሮ ከፍቶ አስገባውና መልሶ ሄደ፡፡
ሲገባ የገጠመው ግዙፍና ግርማ ሞገስ ያለው ቢሮ ነው፡፡እዚህ ቀፋፊ ወህኒ ቤት ውስጥ እንዲህ አይነት የሚያምር ቢሮ ይኖራል ብሎ ገምቶ አያውቅም፡፡ፀጉራቸው ሙሉ በሙሉ ቀለሙን ቀይሮ ነጭ የሆነው ግዙፉ ጠይም ቆፍታምና ሰው ከግዙፉ ጠረጴዛ ኃላ ባለ የቆዳ ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጠው ይታያሉ….በጎርናና እና ሻካራ ድምጻቸው ‹‹ግባ አቶ ሚካኤል…..››አሉት
ሄደና ወደእሳቸው ቀርቦ ለሰላምታ እጁን ዘረጋላቸው…በመጠኑ ከመቀመጫቸው እንደመነሳት አሉና እጃቸውን ዘርግተው ጨበጡትና‹‹ተቀመጥ አቶ ሚካኤል›
እሺ ብሎ አንዱን ወንበር ሳበና ተቀመጠ‹‹ኩማንደር ስለአስቸገርኩት ይቅርታ….ያው የቤተሰብ ጉዳይ ስለሆነብኝ ነው››ሲል ተናገረ፡፡
‹‹ይገባኛል…እንደውም ጥሩ ልጅ ስለሆንክ መመስገን አለብህ…መቼስ ማረሚያ ቤታችን በአባትህ ላይ የወሰደው አቋም ለምን እንደሆነ ይገባሀል አይደል?አዎ ይገባሀል እንጂ …በእኛ ልትበሳጭ ፍፅም አትችልም፡፡››
‹‹አዎ በትክክል ይገባኛል….››ሲል በአጭሩ መለሰ፡፡
‹‹አሁን ያው ከአንተ ጋር እየተነጋገርን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን ሁኔታዎችን ለማስተካከል እንሞክራለን….ዋናው አንተ አባትህንን ምን ያህል ?ማገዝ ትፈልገለህ የሚለው ነው››አሉና ፈገግ ብለው በሲጋራ የበለዘ ጥርሳቸውን አሳዩት፡፡
‹‹ኮማንደር አባቴ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት መሞቻ ቀኑን የሚጠብቅ ሰው ነው…እና ያ ቀን አስኪደርስ ድረስ በተቻለ መጠን በተመቻቸ ሁኔታ እንዲያሳልፍ ማንኛውንም ነገር ለማድረግ ፍቃደኛ ነኝ፡፡አባቴ ይሄንን ቀፋፊ ወንጀል ሰርቶ ወህኒ ቤት ከመግቱ በፊት ለቤተቡ አይደለም ቸገረኝ ላለ ሰው ሁሉ ልብ የሚያዝንና እጁ የሚፈታ መልካምና የተከበረ ሰው ነበር…..ምንም ሆነ ምንም ፍፃሚዊ እንዲህ አሳዛኝ መሆን የለበትም፡፡
‹‹ጥሩ እንደዛ ከሆነ ማድረግ ይምንችለውን ሁሉ እናያለን፡፡››አሉን ወደፊት ተንጠራርተው መጥሪያውን ተጫኑ..አንድ ፖሊስ መጣና ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠ…‹‹ሳጂን ታራሚ ቅጣውን እዚህ አስመጣልን››ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡ
ፖሊሱ ትዕዛዙን ተቀበለና ተመልሶ ወጥቶ ሄደ….ከ5 ደቂቃ በኃላ እስከአሁን ያለሳተዋለው በኩማንደሩ መቀመጫ በቀኝ በኩል የምትገኝ ጠበብ የጀርባ በራፍ ተቆረቀረ…ኮማንደሩ ዝርጥት ሰውነታቸው እየከበዳቸው በመከራ ተነሱና በራፉ ከውስጥ ከፍተው ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ አይኖቹን የተከፈተው በራፍ ላይ እንደተከለ መጠበቅ ጀመረ…ሰው ከማየቱበፊት ብረት ቅጭልጭልታ በጇሮው ሞላ..…ከዛ በተቀመጠበት ደንዝዞ ቀረ..አባቱን ከስድስት ወራት በፊት ነው ያየው…ሰው በስድስት ወር በዚህ መጠና ሊቀየር እንደሚችል ግምቱ የለውም ፡ፀጉሩ ተንጨፍርሮ ተንጨፍርሮ ጉድሮ ሆኖ ግንባሩ ላይ ተደፍቷል…ፂሙ አድጎ ግማሽ ፊቱን ሸፍኖት ያረጀ አንበሳ አስመስሎታል…ከመክሳቱ የተነሳ ሁለቱ ጉንጮቹ አንድ ላይ የተጣበቁ ይመስላል፡፡አይኖቹ ጥልቅ ጉድጓዱ ውስጥ ያሉ ደማቅ አንፖሎች ነው የሚመስሉት…ሚካኤል እንባው ዝርግፍ አለ..ኮማደሩ ከተቀመጡበት ተነሱና ..ለብቻችሁ ጊዜ ልስጣችሁ..አንድሰዓት አላችሁ……በፊት ለፊተኛው በራፍ ክፉሉን ለቀውላቸው ወጡና ከውጭ ቀርቅረውባቸው ብቻቸውን ተዋቸው…
እንደምንም እራሱን አበረታቶ ከተቀመጠበት ተነሳና ወደአባቱ ሄደ…ልጅ እያለ ባለግርማ ሞገሳሙ አባቱ ወደ ቤት መምጣቱን የሚያውቀው የመኪናውን ክላክስ ሲሰማ ነበር..ካዛ ከወንድሙ ጋር ሮጠው ከቤት ይወጡና ወደእሱ ይንደረደራሉ…ከዛ ለልጆቹ የገዛላቸውን ፍራፍሬ ወይም ሌሎች ጣፍጭ ነገሮች የያዘ ፔስታል ይዞ ከመኪናው ሲወርድ እሱን ጨምሮ ሶስቱም ልጆቹ በሽሚያ አንዱ ቀኝ እግሩን ሌላው ግራ እሩን ያቅፍትና በልዩ ፈንጠዝያ ይቀበሉታል…እሱም ስራቸው ይንበረከክና አንዱን ጉንጩን ሌላዋን ግንባሩን እያሳመና እየዳበሰ ይዞቸው ወደቤት ይገባል…አባትዬው ለልጆቹ እንስፍስፍ የሚባል አባት ነበር..በተለይ ዬቱ ታላቅ የሆነችውን ሴት ልጁን በልዩነት ንው የሚወዳት…እሷም በአባቷ በምንም አይነት ሁኔታ የማትደራደር የእሱ ተመራጭ ልጅ ነበረች…እና እንደዛ ኩሩና ሽቅርቅር የነበረው አባቱ አሁን አፅሙ ብቻ ነው ያለው..ሄዶ በፍራቻ ተጠመጠመበት.. ጠረኑ ወደኃላ ይገፋተራል…አባትዬው ምንም አይነት ምላሽ አላሳየውም..እየጎተተ ወደወንበሮቹ ወሰደውና አስቀመጠውና ከፊት ለፊቱ ተቀመጠ፡፡
‹‹አባዬ እንዴት ነህ?››
ለእሱ መልስ ከመስጠት ይልቅ ‹‹ለምን እንደዚህ አደረክ?››ሲል አንቧረቀበት፡፡
‹‹ማለት? ምን አደረኩ?››ምን ስህተት እንደሰራ ባለማወቅ በፍራቻ ጠየቀ፡፡
‹‹ለምን አገኘኸኝ..?እንዴት እንደተቀጣሁና ምን አይነት ቀፋፊ አውሬ እንደሆንኩ ለማየት ነው የመጣኸው?››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ሚካኤል ከወህኒ ቤት እንደመጣ ቀጥታ ወደሰፈር ነው ያመራው፡፡ወደቤት ሲገባ አዲስ አለም ከልጇ ጋር እየተዳረቀች ሳሎን ውስጥ ቢያገኛትም ማንኛቸውንም ምንም ሳያናግር ቀጥታ ወደመኝታ ቤት ነበር የተንደረደረው፡፡
‹‹ሚኪ…ምን ሆነሀል.?.ዛሬ ደግሞ ሰላምታ የለም እንዴ?››
‹‹መጣሁ..››ብሎ ብቻ ወደመኝታ ቤት ገባ…አባቱ የነገሩትን ፎቶ ከግድግዳ ላይ አነሳ ..ከግድግዳው ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ነው…በቀላሉ በእጅ የሚፈረከስ አይነት አይደለም…ከእንደገና ተነደርድሮ ወጣና በጓሮ በኩል ወደ ገራጅ በመሄድ መዶሻ እና መሮ ይዞ መጣ….‹‹አዲስ አለም ቅዱስን ከወለሉ ላይ አንስታ አቀፈችውና ወደመኝታ ቤቱ ተንቀሳቀሰች…እሷ ከመድረሷ በፊት ሚካኤል ወደውስጥ ገብቶ ከውስጥ ዘጋባት
‹‹እንዴ ሚኪ….ምን እየሆንክ ነው…?ለምንድነው የምትዘጋብን?››
‹‹አዲስ..እባክሽ ጥቂት ደቂቃዎችን ስጪኝ……››ብሎ መሮውንና መዶሻውን በመጠቀም ግድግዳውን መቆርቆር ጀመረ…ግድግዳ ውስጥ የተቀመጠውን የአባቱን ሚስጥራዊ እቃ ለማግኘት 3 ደቃቃ ያህል ፈጀበት…በላስቲክ በስነሰርአት የተጠቀለለ ነው፡፡አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠና የላስቲኩን እሽግ ፈቶ አልጋው ላይ ዘረገፈው፡፡….አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች አንድ ሜሞሪ ካርድ ..አንድ ደብዳቤ ነው፡፡፡
መጀመሪያ ፎቶዎቹን አነሳና ተራ በተራ መመልከት ጀመረ…የመጀመሪያው ፎቶ ላይ አናትዬው የሆነ ሰው ክንድ ላይ ተደግፋ በፈገግታ ስትፍለቀለቅ ይታያል..ጭንቅላቱን የሆነ መርፌ ነገር ጠቅ አደረገው….ይሄ ሰው በህይወት ዘመኑ አይቶት አያውቅም…የእናቱን ዘመዶች ሁሉንም ያውቃል…ታዲያ ይሄ ማን ነው?፡፡ሁለተኛውን ፎቶ ገለጠና ተመለከተ…እናትዬው እነሱን ከመውለዷ በፊት ገና ጨቅላ ወጣት ሆና የተነሳቸው ፎቶ ነው..ግን አሁንም ያው ሰው አንገቷ ላይ ተጠምጥሞ በፍቅር ጉንጯን ሲስማት ይታያል…ፎቶውን ገለበጠው…ልቅም ባለ የእጅ ፅሁፍ በአንድ መስመር የተፃፈ ፅሁፍ አለ ‹‹ንጥፍ ወርቅ ፍቅሬ በጣም አፈቅርሻለው….ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡››ይላል፡፡
ሁሉንም ፎቶዎች በየተራ እየገለባበጠ ተመለከተው…ተመሳሳይ የሁለቱ ፎቶ ነው…ሲላፉ ሲሳሳሙ….ሲጎራረሱ የተነሱት ፎቶ ነው፡፡
ቤታቸው የወላጆቻቸውን ትዝታ የሚዘክሩ ሁለት ግዙፍ የፎቶ አልበሞች እዳሉ ያውቃል….እናትና እህቱ በአሰቃቂ ሁኔታ ከሞቱ በኃላ በጣም ሲከፋውና ትዝ ሲሉት ለብቻው ክፍል ዘግቶ ተደብቆ ይመለከት ነበር፡፡እና እዛ አልበም ውሰጥ ዘጠና ፐርሰንት ፎቶ የእሱና የእህትና ወንድሙ ፎቶዎች ፤የበዓል ዝግጅት ፤ የህፃናቱ የልደት በዓል ማስታወሻ ናቸው የሞሉት..እናትና አባቱ በልጆቹ የደስታ ድባብ ውስጥ እንደድምቀት እዚህም እዛም ጣል ተደርገው የተነሱት ነው እንጂ እንዲህ እናቱ ከሌላው ሰውዬ ጋር እንዳደረገችው አይነት አማላይ ፎቶዎች ተነስተው አላየም፡፡
ፎቶውን አስቀመጠና ወረቀቱን አንስቶ አነበበው…
ይድረስ ለምወድሽ ፍቅሬ ንጥፍ ወርቅ …
ይህንን ደብዳቤ ስፅፍልሽ ከአይኖቼ እንባ ሳይሆን ደም እያፈሰስኩ ነው፡፡ ታውቂያለሽ እኔ ከኤለመንተሪ ጀምሮ በጣም ነው የማፈቅርሽ..አንቺም እንደምታፈቅሪኝ አውቃለው፡፡ብዙ አቅድና ብዙ ፕሮግራም ነበረን፡፡በቅርብም ለመጋባት ተነጋግረንና ተማምለን ነበር፡፡አሁን ግን ያንን ቃሌን ማክበር አልችልም፡፡አባዬ ምን ያህል ኃይለኛ እና ጥብቅ ሰው እንደሆነ ታውቂያለሽ ..አሁን አሜሪካ ካለው ወንድሙ ጋር ተነጋግሮ አሜሪካ እንድሄድ ወስኖ ሁሉም ፕሮሰሶች ጨርሶ ሊልከኛ ነው…ማለቴ… አሁን ይሄ ደብዳቤ ሲደርስሽ ምን አልባት እኔ በርሬም ሊሆን ይችላል፡፡
ይቅር በይኛ…..ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡ይላል
እዛ ደብዳቤ ላይ ብዙ የተንጠባጠቡ የእንባ ጠብታዎች ይታያሉ፡፡ሚካኤል ያየውም ሆነ ያነበበው ነገር ምንም እየገባው አይደለም..ከውጭ ደግሞ አዲስአለም የመኝታ ቤቱን በራፍ እየቆረቆረች እየረበሸችው ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ሄዶ በራፉን ከፈተ፡፡ በራፉ ላይ ልጇን አቅፋ ተገተትራ በድንጋጤ በድን የሆነችውን አዲስ አለም ላይ አፈጠጠባት፡፡
‹‹አዲስ ምንድነው?››
‹‹እንዴት መኝታ ቤቱን በላይህ ላይ ዘግተህ ምን እያደረክ ነው?››በስጋትና በፍራቻ ተወጥራ ጠየቀችው፡፡
ዠ
‹‹ኡፍ …ስራ ይዣለሁ ስልሽ አትሰሚም…..ባክሽ አትረብሺኝ››በማለት አንቧረቀና መልሶ ዘጋባት፡፡ከዛ ወደአልጋው ተመለሰ፡፡አዲስአለም በመጀመሪያ ከደነገጠችውን በላይ ደነገጠች…ሚካኤል ምንም ባልገባት ነገር እንዲህ አመናጭቋት አያውቅም፡፡
ወደሳሎን ተመለሰችና ፀአዳ ጋር ደወለችላት፡፡
ስታወራ ድምፃ ይንቀጠቀጣል‹‹ሄሎ ፀዲ..አሁኑኑ ወደቤት ነይ››
‹‹እንዴ ምን ሆንሽ..?
ቅዱስ አመመው እንዴ?››
‹‹አይደለም..አባትዬው ነው፡፡››
ፀአዳ በጣም ደነገጠች‹‹እንዴ ሚኪ ምን ሆነ?››
‹‹እኔ እንጃለት… ቅድም አንቺ ጋር የመጣሁ ጊዜ አባቱን ለመጠየቅ ወህኒ ቤት ሄዶ ነበር…ከዛ ሲመለስ እንደእብድ አድርጎት መኝታ ቤቱ ገባ..ከዛ ወጣና መዶሻና መሮ ይዞ ገብቶ በራፉን ከውስጥ በመዝጋት ግድግዳውን ሲነድለው ነበር…አንኳኩቼ ምን እንደሆነ ስጠይቀው አጓርቶብኝ መልሶ ዘጋው…እህቴ ቶሎ ድረሺኝ…የቀትር ጂኒ ሳያጠናግረው አይቀርም››
‹‹ስለአባቱ መጥፎ ነገር ሰምቶ ይሆን እንዴ?››
‹‹መሰለኝ….ወይ በፈጣሪ ምን አልባት እዛ ሲደርሰ ገድለዋቸው እንዳይሆን ነው የምፈራው..እንደዛ ቢሆንስ በራፍ አስዘግቶ ግድግዳ ያስንዳል እንዴ…?››
‹‹በቃ መጣሁ ..እስከዛው ተረጋጊ››አለቻትና ስልኩን ከመዝጋቷ በፊት ቦርሳውን አንጠለጠለችና መንገድ ጀመረች፡፡
ሚካኤል ሜሞሪውን አነሳና ስልኩ ውስጥ ከተተው፡፡ሁለት ፎልደሮች አሉት፡፡አንደኛውን ከፈተ ….በምስሉ በቅድሚያ ምትታየው እናቱ ነች፡፡አዎ ቡቲክ ቤታቸው ውስጥ ሆና ልብሶችን ሰታስተካከል ይታያል…ወዲያው አንድ በእሷ እድሜ ያለ ሰው መጣ …የሰውዬው ጀርባው ነው ሚታዬው እናትዬው ግን በሰውዬው መምጣት ስትደነግጥ ይታያል፡፡
‹‹ለሚ እንዴት መጣህ?››አገላብጣ እየሰማችው ትጠይቀዋለች፡፡
‹‹እንዴት መጣህ ነው እንኳን ደህና መጣህ ነው የሚባለው?እዚህ ስብሰባ ነበረን …ሳላይሽ ተመልሼ መሄድ አልቻልኩም›››
‹‹እንዴ ከሶስት ቀን በኃላ ቀጠሮ ነበረን እኮ…››
‹‹እሱም እንዳለ ነው…ግን እኔ እኮ በየቀኑ ላገኝሽ ነው የምፈልገው…እንደውም ሙሉ በሙሉ የእኔ እንድትሆኚ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹እሱንማ አስረግዘኘኝ ጥለኸኝ አሜሪካ ከመሄድህ በፊት ማሰብ ነበረብህ፡፡››
‹‹ይሄንን እኮ ብዙ ጊዜ ተነጋግረንበት ሁኔታውን አስረድቼሽ ይቅር ብለሽኛል..አይደል እንዴ የእኔ ፍቅር?››
‹‹አዎ ግን …ይቅር አልኩህ ማለት ለአመታት የገነባሁት ትዳሬንና ልጆቼን በትኜ ወደአንተ ለመመለስ እፈልጋለው ማለት አይደለም፡፡››
‹‹ልጆችሽን በትኚ አልልኩም እኮ ….ባልሽን ፍቺና ልጆቹን ይዘሽ ነይ ነው፡፡›››
‹‹አይ ያንን ሳደርግ ቅጣው እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ይመስልሀል….?እሱ ምንም እንከን የማይወጣለት ድንቅ አባትና ምርጥ ባል ነው፡፡ልጆቹን እንዴት እንደሚወድ እና እንዴት እንደሚንከባከብ ብታውቅ እንዲህ ለማለት አትደፍርም..በተለይ ትርሲትን በልዩ ሁኔታ ነው የሚወዳት…ሲጠራት እኮ እናቴ ነው የሚላት…እሷስ ብትል..?››
‹‹ግን እውነተኛ ልጁ አይደለችም…ትርሲት የእኔ ልጅ ነች፡፡››
ሚካኤል በሚሰማው ነገር ሆዱ ሲገለባበጥ ይታወቀዋል…አረ እንደውም ሊያስታውከው እየተናነቀው ነው፡፡
‹‹አረ ድምጽህን ቀንስ..ድንገት ሰው ቢሰማህስ?››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ሚካኤል ከወህኒ ቤት እንደመጣ ቀጥታ ወደሰፈር ነው ያመራው፡፡ወደቤት ሲገባ አዲስ አለም ከልጇ ጋር እየተዳረቀች ሳሎን ውስጥ ቢያገኛትም ማንኛቸውንም ምንም ሳያናግር ቀጥታ ወደመኝታ ቤት ነበር የተንደረደረው፡፡
‹‹ሚኪ…ምን ሆነሀል.?.ዛሬ ደግሞ ሰላምታ የለም እንዴ?››
‹‹መጣሁ..››ብሎ ብቻ ወደመኝታ ቤት ገባ…አባቱ የነገሩትን ፎቶ ከግድግዳ ላይ አነሳ ..ከግድግዳው ጋር ተመሳስሎ የተሰራ ነው…በቀላሉ በእጅ የሚፈረከስ አይነት አይደለም…ከእንደገና ተነደርድሮ ወጣና በጓሮ በኩል ወደ ገራጅ በመሄድ መዶሻ እና መሮ ይዞ መጣ….‹‹አዲስ አለም ቅዱስን ከወለሉ ላይ አንስታ አቀፈችውና ወደመኝታ ቤቱ ተንቀሳቀሰች…እሷ ከመድረሷ በፊት ሚካኤል ወደውስጥ ገብቶ ከውስጥ ዘጋባት
‹‹እንዴ ሚኪ….ምን እየሆንክ ነው…?ለምንድነው የምትዘጋብን?››
‹‹አዲስ..እባክሽ ጥቂት ደቂቃዎችን ስጪኝ……››ብሎ መሮውንና መዶሻውን በመጠቀም ግድግዳውን መቆርቆር ጀመረ…ግድግዳ ውስጥ የተቀመጠውን የአባቱን ሚስጥራዊ እቃ ለማግኘት 3 ደቃቃ ያህል ፈጀበት…በላስቲክ በስነሰርአት የተጠቀለለ ነው፡፡አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠና የላስቲኩን እሽግ ፈቶ አልጋው ላይ ዘረገፈው፡፡….አምስት የሚሆኑ ፎቶዎች አንድ ሜሞሪ ካርድ ..አንድ ደብዳቤ ነው፡፡፡
መጀመሪያ ፎቶዎቹን አነሳና ተራ በተራ መመልከት ጀመረ…የመጀመሪያው ፎቶ ላይ አናትዬው የሆነ ሰው ክንድ ላይ ተደግፋ በፈገግታ ስትፍለቀለቅ ይታያል..ጭንቅላቱን የሆነ መርፌ ነገር ጠቅ አደረገው….ይሄ ሰው በህይወት ዘመኑ አይቶት አያውቅም…የእናቱን ዘመዶች ሁሉንም ያውቃል…ታዲያ ይሄ ማን ነው?፡፡ሁለተኛውን ፎቶ ገለጠና ተመለከተ…እናትዬው እነሱን ከመውለዷ በፊት ገና ጨቅላ ወጣት ሆና የተነሳቸው ፎቶ ነው..ግን አሁንም ያው ሰው አንገቷ ላይ ተጠምጥሞ በፍቅር ጉንጯን ሲስማት ይታያል…ፎቶውን ገለበጠው…ልቅም ባለ የእጅ ፅሁፍ በአንድ መስመር የተፃፈ ፅሁፍ አለ ‹‹ንጥፍ ወርቅ ፍቅሬ በጣም አፈቅርሻለው….ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡››ይላል፡፡
ሁሉንም ፎቶዎች በየተራ እየገለባበጠ ተመለከተው…ተመሳሳይ የሁለቱ ፎቶ ነው…ሲላፉ ሲሳሳሙ….ሲጎራረሱ የተነሱት ፎቶ ነው፡፡
ቤታቸው የወላጆቻቸውን ትዝታ የሚዘክሩ ሁለት ግዙፍ የፎቶ አልበሞች እዳሉ ያውቃል….እናትና እህቱ በአሰቃቂ ሁኔታ ከሞቱ በኃላ በጣም ሲከፋውና ትዝ ሲሉት ለብቻው ክፍል ዘግቶ ተደብቆ ይመለከት ነበር፡፡እና እዛ አልበም ውሰጥ ዘጠና ፐርሰንት ፎቶ የእሱና የእህትና ወንድሙ ፎቶዎች ፤የበዓል ዝግጅት ፤ የህፃናቱ የልደት በዓል ማስታወሻ ናቸው የሞሉት..እናትና አባቱ በልጆቹ የደስታ ድባብ ውስጥ እንደድምቀት እዚህም እዛም ጣል ተደርገው የተነሱት ነው እንጂ እንዲህ እናቱ ከሌላው ሰውዬ ጋር እንዳደረገችው አይነት አማላይ ፎቶዎች ተነስተው አላየም፡፡
ፎቶውን አስቀመጠና ወረቀቱን አንስቶ አነበበው…
ይድረስ ለምወድሽ ፍቅሬ ንጥፍ ወርቅ …
ይህንን ደብዳቤ ስፅፍልሽ ከአይኖቼ እንባ ሳይሆን ደም እያፈሰስኩ ነው፡፡ ታውቂያለሽ እኔ ከኤለመንተሪ ጀምሮ በጣም ነው የማፈቅርሽ..አንቺም እንደምታፈቅሪኝ አውቃለው፡፡ብዙ አቅድና ብዙ ፕሮግራም ነበረን፡፡በቅርብም ለመጋባት ተነጋግረንና ተማምለን ነበር፡፡አሁን ግን ያንን ቃሌን ማክበር አልችልም፡፡አባዬ ምን ያህል ኃይለኛ እና ጥብቅ ሰው እንደሆነ ታውቂያለሽ ..አሁን አሜሪካ ካለው ወንድሙ ጋር ተነጋግሮ አሜሪካ እንድሄድ ወስኖ ሁሉም ፕሮሰሶች ጨርሶ ሊልከኛ ነው…ማለቴ… አሁን ይሄ ደብዳቤ ሲደርስሽ ምን አልባት እኔ በርሬም ሊሆን ይችላል፡፡
ይቅር በይኛ…..ያንቺው ለሚ በቀለ፡፡ይላል
እዛ ደብዳቤ ላይ ብዙ የተንጠባጠቡ የእንባ ጠብታዎች ይታያሉ፡፡ሚካኤል ያየውም ሆነ ያነበበው ነገር ምንም እየገባው አይደለም..ከውጭ ደግሞ አዲስአለም የመኝታ ቤቱን በራፍ እየቆረቆረች እየረበሸችው ነው፡፡ከተቀመጠበት ተነሳና ሄዶ በራፉን ከፈተ፡፡ በራፉ ላይ ልጇን አቅፋ ተገተትራ በድንጋጤ በድን የሆነችውን አዲስ አለም ላይ አፈጠጠባት፡፡
‹‹አዲስ ምንድነው?››
‹‹እንዴት መኝታ ቤቱን በላይህ ላይ ዘግተህ ምን እያደረክ ነው?››በስጋትና በፍራቻ ተወጥራ ጠየቀችው፡፡
ዠ
‹‹ኡፍ …ስራ ይዣለሁ ስልሽ አትሰሚም…..ባክሽ አትረብሺኝ››በማለት አንቧረቀና መልሶ ዘጋባት፡፡ከዛ ወደአልጋው ተመለሰ፡፡አዲስአለም በመጀመሪያ ከደነገጠችውን በላይ ደነገጠች…ሚካኤል ምንም ባልገባት ነገር እንዲህ አመናጭቋት አያውቅም፡፡
ወደሳሎን ተመለሰችና ፀአዳ ጋር ደወለችላት፡፡
ስታወራ ድምፃ ይንቀጠቀጣል‹‹ሄሎ ፀዲ..አሁኑኑ ወደቤት ነይ››
‹‹እንዴ ምን ሆንሽ..?
ቅዱስ አመመው እንዴ?››
‹‹አይደለም..አባትዬው ነው፡፡››
ፀአዳ በጣም ደነገጠች‹‹እንዴ ሚኪ ምን ሆነ?››
‹‹እኔ እንጃለት… ቅድም አንቺ ጋር የመጣሁ ጊዜ አባቱን ለመጠየቅ ወህኒ ቤት ሄዶ ነበር…ከዛ ሲመለስ እንደእብድ አድርጎት መኝታ ቤቱ ገባ..ከዛ ወጣና መዶሻና መሮ ይዞ ገብቶ በራፉን ከውስጥ በመዝጋት ግድግዳውን ሲነድለው ነበር…አንኳኩቼ ምን እንደሆነ ስጠይቀው አጓርቶብኝ መልሶ ዘጋው…እህቴ ቶሎ ድረሺኝ…የቀትር ጂኒ ሳያጠናግረው አይቀርም››
‹‹ስለአባቱ መጥፎ ነገር ሰምቶ ይሆን እንዴ?››
‹‹መሰለኝ….ወይ በፈጣሪ ምን አልባት እዛ ሲደርሰ ገድለዋቸው እንዳይሆን ነው የምፈራው..እንደዛ ቢሆንስ በራፍ አስዘግቶ ግድግዳ ያስንዳል እንዴ…?››
‹‹በቃ መጣሁ ..እስከዛው ተረጋጊ››አለቻትና ስልኩን ከመዝጋቷ በፊት ቦርሳውን አንጠለጠለችና መንገድ ጀመረች፡፡
ሚካኤል ሜሞሪውን አነሳና ስልኩ ውስጥ ከተተው፡፡ሁለት ፎልደሮች አሉት፡፡አንደኛውን ከፈተ ….በምስሉ በቅድሚያ ምትታየው እናቱ ነች፡፡አዎ ቡቲክ ቤታቸው ውስጥ ሆና ልብሶችን ሰታስተካከል ይታያል…ወዲያው አንድ በእሷ እድሜ ያለ ሰው መጣ …የሰውዬው ጀርባው ነው ሚታዬው እናትዬው ግን በሰውዬው መምጣት ስትደነግጥ ይታያል፡፡
‹‹ለሚ እንዴት መጣህ?››አገላብጣ እየሰማችው ትጠይቀዋለች፡፡
‹‹እንዴት መጣህ ነው እንኳን ደህና መጣህ ነው የሚባለው?እዚህ ስብሰባ ነበረን …ሳላይሽ ተመልሼ መሄድ አልቻልኩም›››
‹‹እንዴ ከሶስት ቀን በኃላ ቀጠሮ ነበረን እኮ…››
‹‹እሱም እንዳለ ነው…ግን እኔ እኮ በየቀኑ ላገኝሽ ነው የምፈልገው…እንደውም ሙሉ በሙሉ የእኔ እንድትሆኚ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹እሱንማ አስረግዘኘኝ ጥለኸኝ አሜሪካ ከመሄድህ በፊት ማሰብ ነበረብህ፡፡››
‹‹ይሄንን እኮ ብዙ ጊዜ ተነጋግረንበት ሁኔታውን አስረድቼሽ ይቅር ብለሽኛል..አይደል እንዴ የእኔ ፍቅር?››
‹‹አዎ ግን …ይቅር አልኩህ ማለት ለአመታት የገነባሁት ትዳሬንና ልጆቼን በትኜ ወደአንተ ለመመለስ እፈልጋለው ማለት አይደለም፡፡››
‹‹ልጆችሽን በትኚ አልልኩም እኮ ….ባልሽን ፍቺና ልጆቹን ይዘሽ ነይ ነው፡፡›››
‹‹አይ ያንን ሳደርግ ቅጣው እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ይመስልሀል….?እሱ ምንም እንከን የማይወጣለት ድንቅ አባትና ምርጥ ባል ነው፡፡ልጆቹን እንዴት እንደሚወድ እና እንዴት እንደሚንከባከብ ብታውቅ እንዲህ ለማለት አትደፍርም..በተለይ ትርሲትን በልዩ ሁኔታ ነው የሚወዳት…ሲጠራት እኮ እናቴ ነው የሚላት…እሷስ ብትል..?››
‹‹ግን እውነተኛ ልጁ አይደለችም…ትርሲት የእኔ ልጅ ነች፡፡››
ሚካኤል በሚሰማው ነገር ሆዱ ሲገለባበጥ ይታወቀዋል…አረ እንደውም ሊያስታውከው እየተናነቀው ነው፡፡
‹‹አረ ድምጽህን ቀንስ..ድንገት ሰው ቢሰማህስ?››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ሚካኤልና ፀአዳ አንድ ሬስቷራንት ቁጭ ብለው ተፋጠዋል፡፡ከሁለቱም ፊት ለፊት ተከፍቶ የተቀመጠ ቢራ አለ..አንዳቸውም ግን አንስተው አልተጎነጩለትም፡፡
‹‹ለምን ጊዜችንን ትጨርሳለህ…የሆንከውን ካልነገርከኝ እንደማለቅህ ታውቃለህ››
‹‹ፀዲ..ለምን ችክ ትያለሽ..?ምንም አልሆንኩ የስራ ጉዳይ ነው አልኩሽ እኮ››
‹‹እኮ ግድግዳ በመዶሻ የሚያስነድል ምን አይነት የስራ ጉዳይ ነው?፡፡ሚኪ እኔ እኮ ለአመታት ነው የማውቀው..አንተን የስራ ጉዳይ በዚህ ልክ ሊያበሳጭህ…ኦረዲ አብደሀል እኮ››
‹‹ተይ ፀዲ አታጋኚ››
‹‹አጋነንኩ እንዴ…?የማትነግረኝ ከሆነ …››አለችና እጇን ወደ ሱሪ ኪሷ ሰዳ ስልኳን አወጣች፡፡
‹‹ምን ልታደርጊ ነው?››ግራ በመጋባት ጠየቃት፡
‹‹ብቻዬን አልቻልኩህም..ለአዲስ ደውልላትና ትምጣ..ከዛ ለሁለት እንሞክርሀለን››
‹‹በፈጠረሽ……የእሷን ጭቅጭቅና ለቅሶ የምሸከምበት ትእግስቱ የለኝም››
‹‹እና ንገረኛ››
‹‹እሺ ነግርሻለው››
ስልኩን ጠረጴዛ ላይ ከቢራ ጠርሙሱ ጎን አስቀመጠችና ሙሉ ትኩረቷን ወደእሱ አደረገች፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ቁዘማ በኋላ እንደምንም አፉን ከፈተ‹‹የአባቴ ጉዳይ ነው››
‹‹እሱንማ አውቄለው…ከዛ ውጭ አንተን በዚህ ልክ ሊረብሽ የሚችል ሌላ ጉዳይ የለም…በዝርዝር ንገረኝ፡፡
‹‹አባቴ እናቴንም ሆነ እህቴን እንዳልገደላቸው ነገረኝ…እኔም አምኜዋለው››
ፀአዳ ክፉኛ ደነገጠች‹‹እና ማን ነው የገደላቸው..?ማለቴ እንዴት ሞቱ?››ተንተባተበች፡፡
‹‹እሱን አላውቅም…አባቴ ግን ከመሞቴ በፊት እናትህንና እህትህን እኔ እንዳልገደልኳቸው በትክክለኛ ማስረጃ አረጋግጥልኝ፡፡ከመሞቴ በፊት ልጆቼ እኔ ንፅህ ሰው መሆኔን ማወቃቸውን ማረጋገጥ እፈልጋለው››አለኝ በማለት ሙሉውን ታሪክ በዝርዝር ነገራት፡፡
‹‹እና አሁን ምን ልታደርግ ነው…?እንዴት አድርህ ማረጋገጥ ትችላለህ?››
‹‹ግድግዳውን የናድኩት ለዛ ነበር..አባቴ እዛ ግድግዳ ውስጥ የደበቃቸው የተወሰኑ ማስረጃዎች ነበሩ..አለና ስልኩን ከፍቶ በሚሞሪ ያሰቀመጣቸውን ቪዲዬዎች አስደመጣት፡፡ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹በጣም ያሳፍራል አይደል?››አላት፡፡
‹‹በእውነት ምን እንደምልህ አላውቅም››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹አየሽ ክህደት ምን እንደሆነ ምን አይነት ህመም እንደሚያስከትል ከእኔ በተሻለ አንቺ ታውቂያሽ..አባቴ እነዚህን ሁሉ መረጃዎች ካወቀ በኋላ ሚስቱ እሱን ሳይሆን ሌላ ሰው እንደምታፈቅር ከተረዳ በኋላ…በጣም የሚወዳት ቀምጥል ልጁ የእሱ ሳትሆን የሌላ ሰው ልጅ እንደሆነች ካወቀ በኃላ ….የሁለት መንታ ወንድ ልጆቹ እናት እሱን ጥላ ወደልጅነት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ዝግጅት ላይ እንዳለች በግልፅ ካወቀ በኋላ ምንድነው ማድረግ ያለበት?ይሄንን ሁሉ በደል እንዴት መቋቋም ይችላል…?እና እሱ ቢቀውስና የእብድ ስራ ቢሰራ ይፈረድበታል?››
‹‹በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው…ግን እኮ አላደረኩትም ብለውሀል….›››
‹‹እሱማ አዎ እወነቱን እንደሆነ ደግሞ እርግጠኛ ነኝ….ግን እንዳውቀው ካስቀመጠልኝ መረጃ አንድም እሱ እንዳለደረገው የሚገልጽ ፍንጭ ማግኘት አልቻልኩም..እና መተንፈስ እስኪያቅተኝ ድረስ በጣም ግራ ተጋብቻለው፡፡
‹‹ምን እንደገረመኝ ታውቃለህ?››አለች፡፡
ትኩረቱን በሙሉ ወደእሷ ሰበሰበና‹‹ምን? ››ሲል ጠየቃት፡፡
አባትህ በግድያው ተጠርጥረው ፍርድ ቤት በሚመላሰሱበት ጊዜ ይሄንን አሁን ለአንተ የሰጡህን መረጃዎች ለምን ለፍርድ ቤቱ አላቀረቧቸውም….ቢያንስ እኮ የተፈረደባቸው የሞት ቅጣት ወደእድሜ ልክ ይቀየርላቸው ነበር፡፡››
‹‹አዎ..ትክክል ነሽ…መረጃዎቹን እንዳገኘው እኔም ወደ አእምሮዬ የመጣው የመጀመሪያ ጥያቄ እሱ ነበር..እና ትናንትና ወደወህኒ ቤት ሄጄ አግኝቼው ነበር….ለምን ለፍርድ ቤት እንደመረጃ አድርገህ አላቀረብከውም ስለው…ለእናንተ ስል?››ሲል መለሰልኝ፡፡
‹‹አልገባኝም… እንዴት ለእኛ ስትል ?››ብየየ መልሼ ጠየቅኩት፡፡
‹‹እንዳልከው ይሄንን ለፍርድ ቤት እንደወንጀል ማቅለያ አድርጌ ባቀርብ ኖሮ ይሄኔ እናትም አባትም ነበር የምታጡት፡፡በወቅቱ የእኛ ቤተሰብ ጉዳይ በየጋዜጣውና መፅኄቱ እንዴት እንደሚፃፍ ታውቃለህ..ይሄ ነገር ወጥቶ ቢሆን ኖሮ ስለእናትህ ምን እንደሚፃፍ አስበው…የተፃፈ ነገር ደግሞ ታሪክ ሆኖ ይቀመጣል…የልጅ ልጇቼ ጭምር ስለወንድ እና ሴት አያታቸው ታሪክ ሲያነብ ምን አይነት የልብ መሰበር ያጋጥማቸዋል…የእኛን ማህበረሰብ ለነገሮች ያለውን ብያኔ የምታውቀው ነው..በእኔ ጉዳይ ምን ያህል ፈተና እና መገለል እንደሚገጥማችሁ አውቃለው…ይሄ የእሷ ታሪክ ቢጨመርበት ኖሮ መግቢያ መውጫ ነው የሚያሳጦችሁ››በማለት መለሰልኝ፡፡
‹‹አይገርምም !!ወላጅ መሆን እኮ እዳ ነው..አንዳንዴ የነፍስ ክፍያ ለመክፈል እንኳን የማታመነታበት ምስጢራዊ ፀጋ ነው፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››
‹‹አሁን አንድ ምርጫ ብቻ ነው ያለን››
በንቃት‹‹ምን ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ሰውዬውን ፈልገን ማነጋገር››
‹‹የትኛውን ሰውዬ?››
ፈራ ተባ እያለች ‹‹የእናትህን ጓደኛ…..››ስትል መለሰችት፡፡
የሚካኤል ደም ስር በንዴት ውጥርጥር አለ‹‹እሱ እኮ ጠላታችን ነው..እዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ ውስጥ የከተተን እሱ ነው…ፊት ለፊት አግኝቼ እንድገድለው ነው የምትፈልጊው፡፡››
‹‹የሆነ ፍንጭ ለማግኘት የግድ እሱን ማግኘት አለብን…የግድ አንተ ልታናግረው አይገባም…ቆይ እስኪ›› አለችና ጠረጴዛ ላይ ያስቀመጠችውን ስልክ አንስታ ከፈተች ..ምን ልታደርግ ነው ብሎ ሲጠብቅ‹‹ስሙ ማን ነበር››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹የማ?››
‹‹የሰውዬው ነዋ››
‹‹ለሚ በቀለ ››
ስሙን ሰርች ላይ ከታ መፈለግ ጀመረች፡፡
የግብርና ሚኒስቴር ዳይሬክተር ዳይሬክቶሪት ደ/ር ለሚ በቀለ የሚል ዜና አየች፡፡
‹‹እንዴ ሰውዬው ባለስልጣን ነው እንዴ?››
ምንም አልመለሰላትም..ዜናውን ከፍታ ለማንበብ ሞከራች…ከአምስት አመት በፊት የተፃፈ ዜና ነው፡እሱን ተወችና ….ሌላ ፈለገች ..ሶስት አራቱን ከከፈተች በኃላ በአራተኛው ትኩረት ሚስብ ዜና አገኘች‹‹የግብርና ሚንስቴሬ ዳይሬክተር ዳይሬክቶሬት የሆኑት ዶ/ር ለሚ በቀለ በጤና እክል ምክንያት መልቀቂያ በማስገባት ስልጣናቸውን ለቀዋል ››ይላል፡፡ከአራት አመት በፊት የተለቀቀ ዜና ነው፡፡
ወደፌስብክ ገባችና በስሙ ፈለገች.. ዲአክቲቬት ከሆነ አመታት አልፈዋል፡፡
‹‹ሰውዬው ጥሩ ሁኔታ ላይ አይመስለኝም….ቆይ ለእኔ ተውልኝ››
‹‹ምን ልታደርጊ አሰብሽ….?››
‹‹ያለን ምርጫ አንድ ብቻ ነው፣ቢያንስ አሁን አንድ ነገር አውቀናል..ከአራት አመት በፊት ግብርና ሚኒስቴር ይሰራ ነበር…ስለዚህ አዛ ሄድና አሁን ሚገኝበትን አድራሻ ጠይቃቸዋለው…ቢያንስ ስልኩን ይሰጡኛል፡፡››
‹‹እስቲ እናያለን››ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡
‹‹አይዞህ ምንም አትጨነቅ..ይሄንን ነገር እንፈታዋለን….የፈለገ መስዋእትነት ያስከፍል የአባትህን ምኞት እናሳካለን….ይሄ ጉዳይ ዘሚካኤልንም ወደቤተሰቦቹ እንዲመለስ ለማድረግ ያግዘን ይሆናል፡፡››
‹‹እኔ እንጇ..ዘሚካኤል እናቱን እንደፈጣሪው ነው የሚወዳት..ለእሱ እሷ እንከን አልባ መልአክ የሆነች ሴት ነች…ይሄንን ሲሰማ ዳግመኛ ይበልጥ እንዳይሰበር ነው የምፈራው፡፡
‹‹አይዞህ ….ከመሰበር በኃላ ያለ መጠገን ነው እኛን ሞርዶ ሙሉ ሰው የሚያደርገን፡፡ደግሞ እናትህ ጥፋት ያጠፋችው በሚስትነቷ ነው እንጂ በእናትነቷ እስከወዲያኛው ምሉ እንደሆነች ነው፡፡››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ሚካኤልና ፀአዳ አንድ ሬስቷራንት ቁጭ ብለው ተፋጠዋል፡፡ከሁለቱም ፊት ለፊት ተከፍቶ የተቀመጠ ቢራ አለ..አንዳቸውም ግን አንስተው አልተጎነጩለትም፡፡
‹‹ለምን ጊዜችንን ትጨርሳለህ…የሆንከውን ካልነገርከኝ እንደማለቅህ ታውቃለህ››
‹‹ፀዲ..ለምን ችክ ትያለሽ..?ምንም አልሆንኩ የስራ ጉዳይ ነው አልኩሽ እኮ››
‹‹እኮ ግድግዳ በመዶሻ የሚያስነድል ምን አይነት የስራ ጉዳይ ነው?፡፡ሚኪ እኔ እኮ ለአመታት ነው የማውቀው..አንተን የስራ ጉዳይ በዚህ ልክ ሊያበሳጭህ…ኦረዲ አብደሀል እኮ››
‹‹ተይ ፀዲ አታጋኚ››
‹‹አጋነንኩ እንዴ…?የማትነግረኝ ከሆነ …››አለችና እጇን ወደ ሱሪ ኪሷ ሰዳ ስልኳን አወጣች፡፡
‹‹ምን ልታደርጊ ነው?››ግራ በመጋባት ጠየቃት፡
‹‹ብቻዬን አልቻልኩህም..ለአዲስ ደውልላትና ትምጣ..ከዛ ለሁለት እንሞክርሀለን››
‹‹በፈጠረሽ……የእሷን ጭቅጭቅና ለቅሶ የምሸከምበት ትእግስቱ የለኝም››
‹‹እና ንገረኛ››
‹‹እሺ ነግርሻለው››
ስልኩን ጠረጴዛ ላይ ከቢራ ጠርሙሱ ጎን አስቀመጠችና ሙሉ ትኩረቷን ወደእሱ አደረገች፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ቁዘማ በኋላ እንደምንም አፉን ከፈተ‹‹የአባቴ ጉዳይ ነው››
‹‹እሱንማ አውቄለው…ከዛ ውጭ አንተን በዚህ ልክ ሊረብሽ የሚችል ሌላ ጉዳይ የለም…በዝርዝር ንገረኝ፡፡
‹‹አባቴ እናቴንም ሆነ እህቴን እንዳልገደላቸው ነገረኝ…እኔም አምኜዋለው››
ፀአዳ ክፉኛ ደነገጠች‹‹እና ማን ነው የገደላቸው..?ማለቴ እንዴት ሞቱ?››ተንተባተበች፡፡
‹‹እሱን አላውቅም…አባቴ ግን ከመሞቴ በፊት እናትህንና እህትህን እኔ እንዳልገደልኳቸው በትክክለኛ ማስረጃ አረጋግጥልኝ፡፡ከመሞቴ በፊት ልጆቼ እኔ ንፅህ ሰው መሆኔን ማወቃቸውን ማረጋገጥ እፈልጋለው››አለኝ በማለት ሙሉውን ታሪክ በዝርዝር ነገራት፡፡
‹‹እና አሁን ምን ልታደርግ ነው…?እንዴት አድርህ ማረጋገጥ ትችላለህ?››
‹‹ግድግዳውን የናድኩት ለዛ ነበር..አባቴ እዛ ግድግዳ ውስጥ የደበቃቸው የተወሰኑ ማስረጃዎች ነበሩ..አለና ስልኩን ከፍቶ በሚሞሪ ያሰቀመጣቸውን ቪዲዬዎች አስደመጣት፡፡ሽምቅቅ አለች፡፡
‹‹በጣም ያሳፍራል አይደል?››አላት፡፡
‹‹በእውነት ምን እንደምልህ አላውቅም››ስትል መለሰችለት፡፡
‹‹አየሽ ክህደት ምን እንደሆነ ምን አይነት ህመም እንደሚያስከትል ከእኔ በተሻለ አንቺ ታውቂያሽ..አባቴ እነዚህን ሁሉ መረጃዎች ካወቀ በኋላ ሚስቱ እሱን ሳይሆን ሌላ ሰው እንደምታፈቅር ከተረዳ በኋላ…በጣም የሚወዳት ቀምጥል ልጁ የእሱ ሳትሆን የሌላ ሰው ልጅ እንደሆነች ካወቀ በኃላ ….የሁለት መንታ ወንድ ልጆቹ እናት እሱን ጥላ ወደልጅነት ፍቅረኛዋ ልትሄድ ዝግጅት ላይ እንዳለች በግልፅ ካወቀ በኋላ ምንድነው ማድረግ ያለበት?ይሄንን ሁሉ በደል እንዴት መቋቋም ይችላል…?እና እሱ ቢቀውስና የእብድ ስራ ቢሰራ ይፈረድበታል?››
‹‹በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው…ግን እኮ አላደረኩትም ብለውሀል….›››
‹‹እሱማ አዎ እወነቱን እንደሆነ ደግሞ እርግጠኛ ነኝ….ግን እንዳውቀው ካስቀመጠልኝ መረጃ አንድም እሱ እንዳለደረገው የሚገልጽ ፍንጭ ማግኘት አልቻልኩም..እና መተንፈስ እስኪያቅተኝ ድረስ በጣም ግራ ተጋብቻለው፡፡
‹‹ምን እንደገረመኝ ታውቃለህ?››አለች፡፡
ትኩረቱን በሙሉ ወደእሷ ሰበሰበና‹‹ምን? ››ሲል ጠየቃት፡፡
አባትህ በግድያው ተጠርጥረው ፍርድ ቤት በሚመላሰሱበት ጊዜ ይሄንን አሁን ለአንተ የሰጡህን መረጃዎች ለምን ለፍርድ ቤቱ አላቀረቧቸውም….ቢያንስ እኮ የተፈረደባቸው የሞት ቅጣት ወደእድሜ ልክ ይቀየርላቸው ነበር፡፡››
‹‹አዎ..ትክክል ነሽ…መረጃዎቹን እንዳገኘው እኔም ወደ አእምሮዬ የመጣው የመጀመሪያ ጥያቄ እሱ ነበር..እና ትናንትና ወደወህኒ ቤት ሄጄ አግኝቼው ነበር….ለምን ለፍርድ ቤት እንደመረጃ አድርገህ አላቀረብከውም ስለው…ለእናንተ ስል?››ሲል መለሰልኝ፡፡
‹‹አልገባኝም… እንዴት ለእኛ ስትል ?››ብየየ መልሼ ጠየቅኩት፡፡
‹‹እንዳልከው ይሄንን ለፍርድ ቤት እንደወንጀል ማቅለያ አድርጌ ባቀርብ ኖሮ ይሄኔ እናትም አባትም ነበር የምታጡት፡፡በወቅቱ የእኛ ቤተሰብ ጉዳይ በየጋዜጣውና መፅኄቱ እንዴት እንደሚፃፍ ታውቃለህ..ይሄ ነገር ወጥቶ ቢሆን ኖሮ ስለእናትህ ምን እንደሚፃፍ አስበው…የተፃፈ ነገር ደግሞ ታሪክ ሆኖ ይቀመጣል…የልጅ ልጇቼ ጭምር ስለወንድ እና ሴት አያታቸው ታሪክ ሲያነብ ምን አይነት የልብ መሰበር ያጋጥማቸዋል…የእኛን ማህበረሰብ ለነገሮች ያለውን ብያኔ የምታውቀው ነው..በእኔ ጉዳይ ምን ያህል ፈተና እና መገለል እንደሚገጥማችሁ አውቃለው…ይሄ የእሷ ታሪክ ቢጨመርበት ኖሮ መግቢያ መውጫ ነው የሚያሳጦችሁ››በማለት መለሰልኝ፡፡
‹‹አይገርምም !!ወላጅ መሆን እኮ እዳ ነው..አንዳንዴ የነፍስ ክፍያ ለመክፈል እንኳን የማታመነታበት ምስጢራዊ ፀጋ ነው፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ››
‹‹አሁን አንድ ምርጫ ብቻ ነው ያለን››
በንቃት‹‹ምን ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ሰውዬውን ፈልገን ማነጋገር››
‹‹የትኛውን ሰውዬ?››
ፈራ ተባ እያለች ‹‹የእናትህን ጓደኛ…..››ስትል መለሰችት፡፡
የሚካኤል ደም ስር በንዴት ውጥርጥር አለ‹‹እሱ እኮ ጠላታችን ነው..እዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ ውስጥ የከተተን እሱ ነው…ፊት ለፊት አግኝቼ እንድገድለው ነው የምትፈልጊው፡፡››
‹‹የሆነ ፍንጭ ለማግኘት የግድ እሱን ማግኘት አለብን…የግድ አንተ ልታናግረው አይገባም…ቆይ እስኪ›› አለችና ጠረጴዛ ላይ ያስቀመጠችውን ስልክ አንስታ ከፈተች ..ምን ልታደርግ ነው ብሎ ሲጠብቅ‹‹ስሙ ማን ነበር››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹የማ?››
‹‹የሰውዬው ነዋ››
‹‹ለሚ በቀለ ››
ስሙን ሰርች ላይ ከታ መፈለግ ጀመረች፡፡
የግብርና ሚኒስቴር ዳይሬክተር ዳይሬክቶሪት ደ/ር ለሚ በቀለ የሚል ዜና አየች፡፡
‹‹እንዴ ሰውዬው ባለስልጣን ነው እንዴ?››
ምንም አልመለሰላትም..ዜናውን ከፍታ ለማንበብ ሞከራች…ከአምስት አመት በፊት የተፃፈ ዜና ነው፡እሱን ተወችና ….ሌላ ፈለገች ..ሶስት አራቱን ከከፈተች በኃላ በአራተኛው ትኩረት ሚስብ ዜና አገኘች‹‹የግብርና ሚንስቴሬ ዳይሬክተር ዳይሬክቶሬት የሆኑት ዶ/ር ለሚ በቀለ በጤና እክል ምክንያት መልቀቂያ በማስገባት ስልጣናቸውን ለቀዋል ››ይላል፡፡ከአራት አመት በፊት የተለቀቀ ዜና ነው፡፡
ወደፌስብክ ገባችና በስሙ ፈለገች.. ዲአክቲቬት ከሆነ አመታት አልፈዋል፡፡
‹‹ሰውዬው ጥሩ ሁኔታ ላይ አይመስለኝም….ቆይ ለእኔ ተውልኝ››
‹‹ምን ልታደርጊ አሰብሽ….?››
‹‹ያለን ምርጫ አንድ ብቻ ነው፣ቢያንስ አሁን አንድ ነገር አውቀናል..ከአራት አመት በፊት ግብርና ሚኒስቴር ይሰራ ነበር…ስለዚህ አዛ ሄድና አሁን ሚገኝበትን አድራሻ ጠይቃቸዋለው…ቢያንስ ስልኩን ይሰጡኛል፡፡››
‹‹እስቲ እናያለን››ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡
‹‹አይዞህ ምንም አትጨነቅ..ይሄንን ነገር እንፈታዋለን….የፈለገ መስዋእትነት ያስከፍል የአባትህን ምኞት እናሳካለን….ይሄ ጉዳይ ዘሚካኤልንም ወደቤተሰቦቹ እንዲመለስ ለማድረግ ያግዘን ይሆናል፡፡››
‹‹እኔ እንጇ..ዘሚካኤል እናቱን እንደፈጣሪው ነው የሚወዳት..ለእሱ እሷ እንከን አልባ መልአክ የሆነች ሴት ነች…ይሄንን ሲሰማ ዳግመኛ ይበልጥ እንዳይሰበር ነው የምፈራው፡፡
‹‹አይዞህ ….ከመሰበር በኃላ ያለ መጠገን ነው እኛን ሞርዶ ሙሉ ሰው የሚያደርገን፡፡ደግሞ እናትህ ጥፋት ያጠፋችው በሚስትነቷ ነው እንጂ በእናትነቷ እስከወዲያኛው ምሉ እንደሆነች ነው፡፡››
#አላገባህም
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁ_ገመቹ
/////
በማግስቱ አቶ ቅጣው እንደተለመደው ጭለማና ድፍን በሆነው የእስር ክፍሉ በሰንሰለት እጅና እግራቸው እንደተጠፈረ ኩርምት ብለው በትካዜ ላይ እያሉ የበራፍ መኳኳት ድምፅ ሰሙ የገመቱት ትንሽዬዋ መስኮት መሳይ ቀዳዳ ተከፍታ የእለቱ የምግብ ኮታቸው ይወረወርልኛል ብለው ነበር …ግን ትልቁ በራፍ ተከፈተ….ወዲያው ብርሀን ሾልኮ ወደክፍሉ ገባና አይናቸው ላይ አንፀባረቀባቸው፡፡አይናቸውን ጨፈኑ..ከዛ ገለጡ… አሁንም ጨፈኑ እንደዛ እያደረጉ ካለማመዱት በኋላ ገልጠው ምን እየተካሄደ እንደሆነ ሲያስተውሉ ከክፍሉ ይዘዋቸው ሊወጡ እንደሆነ ገባቸው..፡፡አንድ ጠባቂ ክላሹን እንዳቀባበለ ውጭ በራፍ ላይ ሲታያቸው አንደኛው ደግሞ እንደተለመደው ወደውስጥ ገባና ሰነሰለቱን ከመሬት ከተቀበረው ብረት ጋር የተያያዘውን ብረት ይፈታል ብለው ሲጠብቁ ከእግራቸው ጋር የተያያዘውን ሰንሰለት ፈታውና አላቀቀው…ከዛ ወደላይ ቀና ብሎ በእጃቸው ላይ የተሳረውን ሰንሰለት በተመሳሳይ ፈታና እዛው ወለሉ ላይ ሲወረውረው የፈጠረው የቅልጭልጭልታ ድምፅ በጆሮቸው ገብቶ አእመሮቸውን አተረማመሰው…‹‹ወደ መገደያዬ ሊወስዱኝ ነው እንዴ?››ሲሉ አሰቡ…..በመጀመሪያ በጣም ቅር አላቸው፡፡ከዛ ግን‹‹እንደውም ግልግል ነው…አሁንስ በህይወት እየኖርኩ ነው ይባላል …?
ከሞት ወደሞት መሄዱ ምኑ ያስፈራል?››ሲሉ አሰቡ፡፡ፊት ለፊታቸው ያለው ፖሊስ ከኪሱ ሌላ የሚያብረቀርቅ ካቴና ከጃኬት ኪሱ አወጣና እጃቸው ላይ ካደረገላቸው በኃላ
‹‹አቶ ቅጣው..ቀጥል እንሂድ..››አላቸው…፡፡
‹‹ለምን..?ወዴየት?› የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ሳይጠይቅ በዝምታ ፊቱን ወደበራፉ አዞረና እርምጃውን ቀጠለ…ሰውነቱ የዶሮ ላባ ያህል ቀለለው…ላለፉት ስድስት ወር እንዛ አስጠሊታ ድምፅ ያላቸው የዛጉ ሰንሰለቶች ከእግሩና ከእጁ ጋር ተላቀው ስለማያውቁ በተንቀሳቀሰ ቁጥር እንሱንም ይዞ ይንቀሳቀስ ስለነበረ እንደራሱ አካል ያያቸው ከጀመረ ሰነባብቶል…እና አሁን የሆነ የአካሉን ክፍል ቆርጠው እንዳስቀሩበት ነው የተሰማው..ከክፍሉ ይዘውት ወጡ ፡፡በኮሪደሩ ይዘውት ከተጓዙ በኋላ ለመጀመሪየ ጊዜ ከዛ ቀፋፊና መቀብር መሳይ ህንፃ ሙሉ በሙሉ ይዘውት ወጡና የውጭን ብርሀን እንዲያይ አደረጉት፡፡በመጀመሪያ ጭው አለበት…ከዛ እንደምንም አይኑን አጨንቁሮ አካባቢውን ለመቃኘት ሞከረ..ዛፎች ይታዩታል….አረንጓዴ ሳር የለበሰ ሜዳ ..ከዛፍ ዛፍ እየበረሩ የሚታዩ ወፎች…በግዙፍ አጥር የተከበበ አነስታኛ ሜዳ…ሜዳውን ሞልተው ኳስ የሚጫወቱና ስፖርት ሚሰሩ እናም ደግሞ አፍ ለአፈ ገጥመው የሚያወሩ ቢጫ ቱታ የለበሱ መአት እስረኞች..ከሁሉም በላይ እምክ እምክ የማይልና የማያፍን ንፅህ የተፈጥሮ አየር በአፍንጫው ሲስብ …በቃ ከመቃብር የወጣ አይነት ስሜት ነው የተሰማው….እንባውን ከትሮ ማቆየት ስለተሳነው አለቀሰ…
‹‹እዛ ጨለማና የታመቀ ክፍል ውስጥ በህይወት ከመቆየት እዚህ በተፈጥሮ ፀጋ በተሸሞነሞነ ንፅህ አየር ውስጥ ሞቶ መቀበር ይሻላል››ሲል አሰበ፡፡
ከፊት እየመራው ያለው ፖሊስ‹‹ቀጥል አቶ ቅጣው››ሲል እንዲከተለው አዘዘው፡፡ ሌለኛው ፖሊስ ከኋላ ክላሹን እንደደቀነበት በሁለት ህንፃዎች መካከል ባለች ጠባብ መንገድ እየመራ ወሰደው.. በቆርቆሮ የተሰሩ ብዙ ክፍል ያሉበት ክፍል ጋር ሲደርስ ቆመ …ይሄን የቆርቆሮ ቤት ያውቀዋል….እስረኞች በእያንዳንዱ ክፍል አምስትና ስድስት እየሆኑ በሳምንት አንድ ቀን ሰውነታቸውን የሚታጠቡበት ክፍል ነው፡፡ከበርካታ ወራት በፊት እሱም እንደማንኛውም እስረኛ በሳምንት አንድ ቀን የመታጠብ ወርቃማ እድል ነበረው…አሁን ግን ሰውነቱ ውሀ ከነካው ስድስት ወር ከማለፉ የተነሳ የሰውነቱ ቀለም ሙሉ በሙሉ ተቀይሮል …አካላቱ ላይ የተለደፈው ቆሻሻ በውሀና ሳሙና ሳይሆን በቢላዋ እየተቀረፈ እየተቀረፈ ካልተነሳ የሚፀዳ አይመስልም፡
አንድ ሌላ ፖሊስ በፔስታል የሆነ ነገር ይዞ በራፍ ላይ እየጠበቃቸው ነበር፡፡መድረሳቸውን ሲያይ አንደኛውን ክፍል ከፈተና ..ይሄው መቀየሬያ ልብሱ እዚህ ውስጥ አለ..ልጅህ ነው ያመጣልህ….ሌላውን ክፍል ድርስ እናመጣልሀለን..ሳሙናም ይሄው አለና›› ለፖሊሱ አስረክቦ ሄደ፡፡
‹‹አቶ ቅጣው ያልሆነ ነገር ለመስራት ፈፅሞ እንዳትሞክር….ይሄው ሳሙና … ሰውነትህን ታጠብና ልብስ ቀይር….››አለው
‹‹ለምን ግን?››ሲል መጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ጠየቀ፡፡
ፖሊሱ እጁ ላይ ያጠለቀለትን ካቴና እየፈታ‹‹ለምን ማለት ..ምኑ?››ሲል ጥያቄው እንዳልገባው በሚገልፅ ሁኔታ መልሶ ጠየቀው፡፡
‹‹መታጠቤና ..ልብስ መቀየሬ?››
‹‹ምነው አሁን ያለህበት ሁኔታ ተመችቶሀል እንዴ?ማጥ ውስጥ ሲንከባለል የከረመ ከርከሮ እኮ ነው የምትመስለው …ለማንኛውም ለምን እንድታጠብ እንደተፈቀደልህ አናውቅም…እኛ የታዘዝነውን እያደረግን ነው…ስራችንን እንድንሰራ ተባበረን..እንካ ልብሱንና ሳሙናውን… ይዘህ ግባ››አለው።
እንዳው በግዴለሽነት ተቀበለውና ወደውስጥ በዝግታ ገብቶ በራፉን ከውስጥ ሊዘጋው ሲል…ፖሊሱ ፈጠን አለና‹‹አይ አትዝጋው…..ክፍት ይሁን …ከእይታችን ውጭ መሆን የለብህም››የሚል ትእዛዝ ሰጠው፡፡
በግዴለሽነት በራፉን መልሶ በልቅጦ ወደውስጥ ገባ…ልብስ የያዘውን ፔስታል በአንዱ የግድግዳው ኮርነር ጋር አስቀምጦ ሳሙናውን ብቻ ይዞ ቀጥታ ሻወር ወደላበት ቦታ ሄደ… ውሀውን እስከመጨረሻ ከፈተውና ውስጡ ቆመ…ውጭ ሆነው በትኩረት እየተከታተሉት ያሉት ሁለት ፖሊሶች በገረሜታ ምን እየሰራነው? ብለው እየተገረሙበት ነበር፡፡ለሀያ ደቂቃ አልተነቃነቀም…ውሀው እየተንፎለፎለ በላዩ ላይ ሲወርድ ከለበሰው ልብስ ላይም ሆነ ከገላው ላይ እየተቀረፈ የሚወርደው ቆሻሻ ለሚያየው ሰው ይዘገንናል..በኋላ ግራ ሲገባቸው አንደኛው ፖሊስ ወደውስጥ ገባና ወደእሱ ተጠግቶ
‹አቶ ቅጣው ..ቅጣው …››ውሀውን ዘጋው ሲል ጠየቀው…ከገባበት ጥልቅ ሰመመን የነቃ የሚመስለው ቅጣው‹‹አቤት በቃ ልውጣ እንዴ?››ሲል ጠየቀ፡፡
‹‹አይ እሱ እስከፈለግክ መታጠብ ትችላለህ..ግን በስርአት አድርገው፡››
‹‹በስርአት ማለት?››ተደነጋገረ፡፡
ሳሙናው እኮ በእጅህ እንደያዝከው ሟሙቶ ሊያልቅ ነው..የለበስከውን ቀፋፊ እና ቡትቶ ልብስ አውጥተህ ጣልና ሰውነትህን ሳሙና እየመታህ በትክክል ታጠብ››
‹‹እ..ገባኝ..እሺ›› ብሎ ልብሶቹን አወላለቀና ከእሱ አርቆ በመወርወር ርቃኑን ቆመና ሻወሩን በድጋሚ ከፈተ…ከዛ ከፀጉሩ በመጀመር ሙሉ ሰውነቱን ሳሙና በመለቅለቅ መታጠብ ጀመረ…ምን አልባትም አምስት ስድስት ጊዜ ደጋግሞ ሳሙና በመለቅለቅ ለወራት በሰውነቱ ተጠቅጥቆ የተከማቸውን ቆሻሻ በተቻለው መልኩ ለማስለቀቅ ጣረ… ከዛ…ቧንቧውን ዘጋና ቀጥታ ወደፔስታሉ በመሄድ ውስጡ ያለውን ልብስ ተራ በተራ እያወጣ በመመልከት ለበሰ…ሁሉም ልብሶች ምርጥና አዲስ ሲሆኑ ለእሱ ግን ሰፍተውታል ….‹‹ምን አልባትም በጣም ከመክሳቴ የተነሳ ለእኔ በልኬ የሚሆን ልብስ ገበያ ላይ ስለሌለ ይሆናል ይሄን ያመጡልኝ››ሲል አሰበና በመጨረሻ ካልሲውንና ጫማውን አድርጎ ወደ ፖሊሶቹ ሄደ….በራፉ ላይ ተቀበሉትና በእጁ ላይ ካቴናውን መልሰው አጠለቁለትና በሌላ አቅጣጫ ይዘውት ሄዱ…አሁንም የወሰዱትን ቦታ ገና እንዳየው ነው ያወቀው›..የእስረኞች ፀጉር ማስተካከያ ቦታ ነው፡፡
‹‹ሽፈራው በል ቆንጆ አድርገህ አስተካክለው››ፖሊሱ ፀጉር አስተካካዩን አዘዘው፡፡
‹‹እንዴ ቅጣው..?እንዴት ነህ..?ሰላም ነህ?››ፀጉር አስተካካዩ በገረሜታ ተቀበለው፡፡
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁ_ገመቹ
/////
በማግስቱ አቶ ቅጣው እንደተለመደው ጭለማና ድፍን በሆነው የእስር ክፍሉ በሰንሰለት እጅና እግራቸው እንደተጠፈረ ኩርምት ብለው በትካዜ ላይ እያሉ የበራፍ መኳኳት ድምፅ ሰሙ የገመቱት ትንሽዬዋ መስኮት መሳይ ቀዳዳ ተከፍታ የእለቱ የምግብ ኮታቸው ይወረወርልኛል ብለው ነበር …ግን ትልቁ በራፍ ተከፈተ….ወዲያው ብርሀን ሾልኮ ወደክፍሉ ገባና አይናቸው ላይ አንፀባረቀባቸው፡፡አይናቸውን ጨፈኑ..ከዛ ገለጡ… አሁንም ጨፈኑ እንደዛ እያደረጉ ካለማመዱት በኋላ ገልጠው ምን እየተካሄደ እንደሆነ ሲያስተውሉ ከክፍሉ ይዘዋቸው ሊወጡ እንደሆነ ገባቸው..፡፡አንድ ጠባቂ ክላሹን እንዳቀባበለ ውጭ በራፍ ላይ ሲታያቸው አንደኛው ደግሞ እንደተለመደው ወደውስጥ ገባና ሰነሰለቱን ከመሬት ከተቀበረው ብረት ጋር የተያያዘውን ብረት ይፈታል ብለው ሲጠብቁ ከእግራቸው ጋር የተያያዘውን ሰንሰለት ፈታውና አላቀቀው…ከዛ ወደላይ ቀና ብሎ በእጃቸው ላይ የተሳረውን ሰንሰለት በተመሳሳይ ፈታና እዛው ወለሉ ላይ ሲወረውረው የፈጠረው የቅልጭልጭልታ ድምፅ በጆሮቸው ገብቶ አእመሮቸውን አተረማመሰው…‹‹ወደ መገደያዬ ሊወስዱኝ ነው እንዴ?››ሲሉ አሰቡ…..በመጀመሪያ በጣም ቅር አላቸው፡፡ከዛ ግን‹‹እንደውም ግልግል ነው…አሁንስ በህይወት እየኖርኩ ነው ይባላል …?
ከሞት ወደሞት መሄዱ ምኑ ያስፈራል?››ሲሉ አሰቡ፡፡ፊት ለፊታቸው ያለው ፖሊስ ከኪሱ ሌላ የሚያብረቀርቅ ካቴና ከጃኬት ኪሱ አወጣና እጃቸው ላይ ካደረገላቸው በኃላ
‹‹አቶ ቅጣው..ቀጥል እንሂድ..››አላቸው…፡፡
‹‹ለምን..?ወዴየት?› የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ሳይጠይቅ በዝምታ ፊቱን ወደበራፉ አዞረና እርምጃውን ቀጠለ…ሰውነቱ የዶሮ ላባ ያህል ቀለለው…ላለፉት ስድስት ወር እንዛ አስጠሊታ ድምፅ ያላቸው የዛጉ ሰንሰለቶች ከእግሩና ከእጁ ጋር ተላቀው ስለማያውቁ በተንቀሳቀሰ ቁጥር እንሱንም ይዞ ይንቀሳቀስ ስለነበረ እንደራሱ አካል ያያቸው ከጀመረ ሰነባብቶል…እና አሁን የሆነ የአካሉን ክፍል ቆርጠው እንዳስቀሩበት ነው የተሰማው..ከክፍሉ ይዘውት ወጡ ፡፡በኮሪደሩ ይዘውት ከተጓዙ በኋላ ለመጀመሪየ ጊዜ ከዛ ቀፋፊና መቀብር መሳይ ህንፃ ሙሉ በሙሉ ይዘውት ወጡና የውጭን ብርሀን እንዲያይ አደረጉት፡፡በመጀመሪያ ጭው አለበት…ከዛ እንደምንም አይኑን አጨንቁሮ አካባቢውን ለመቃኘት ሞከረ..ዛፎች ይታዩታል….አረንጓዴ ሳር የለበሰ ሜዳ ..ከዛፍ ዛፍ እየበረሩ የሚታዩ ወፎች…በግዙፍ አጥር የተከበበ አነስታኛ ሜዳ…ሜዳውን ሞልተው ኳስ የሚጫወቱና ስፖርት ሚሰሩ እናም ደግሞ አፍ ለአፈ ገጥመው የሚያወሩ ቢጫ ቱታ የለበሱ መአት እስረኞች..ከሁሉም በላይ እምክ እምክ የማይልና የማያፍን ንፅህ የተፈጥሮ አየር በአፍንጫው ሲስብ …በቃ ከመቃብር የወጣ አይነት ስሜት ነው የተሰማው….እንባውን ከትሮ ማቆየት ስለተሳነው አለቀሰ…
‹‹እዛ ጨለማና የታመቀ ክፍል ውስጥ በህይወት ከመቆየት እዚህ በተፈጥሮ ፀጋ በተሸሞነሞነ ንፅህ አየር ውስጥ ሞቶ መቀበር ይሻላል››ሲል አሰበ፡፡
ከፊት እየመራው ያለው ፖሊስ‹‹ቀጥል አቶ ቅጣው››ሲል እንዲከተለው አዘዘው፡፡ ሌለኛው ፖሊስ ከኋላ ክላሹን እንደደቀነበት በሁለት ህንፃዎች መካከል ባለች ጠባብ መንገድ እየመራ ወሰደው.. በቆርቆሮ የተሰሩ ብዙ ክፍል ያሉበት ክፍል ጋር ሲደርስ ቆመ …ይሄን የቆርቆሮ ቤት ያውቀዋል….እስረኞች በእያንዳንዱ ክፍል አምስትና ስድስት እየሆኑ በሳምንት አንድ ቀን ሰውነታቸውን የሚታጠቡበት ክፍል ነው፡፡ከበርካታ ወራት በፊት እሱም እንደማንኛውም እስረኛ በሳምንት አንድ ቀን የመታጠብ ወርቃማ እድል ነበረው…አሁን ግን ሰውነቱ ውሀ ከነካው ስድስት ወር ከማለፉ የተነሳ የሰውነቱ ቀለም ሙሉ በሙሉ ተቀይሮል …አካላቱ ላይ የተለደፈው ቆሻሻ በውሀና ሳሙና ሳይሆን በቢላዋ እየተቀረፈ እየተቀረፈ ካልተነሳ የሚፀዳ አይመስልም፡
አንድ ሌላ ፖሊስ በፔስታል የሆነ ነገር ይዞ በራፍ ላይ እየጠበቃቸው ነበር፡፡መድረሳቸውን ሲያይ አንደኛውን ክፍል ከፈተና ..ይሄው መቀየሬያ ልብሱ እዚህ ውስጥ አለ..ልጅህ ነው ያመጣልህ….ሌላውን ክፍል ድርስ እናመጣልሀለን..ሳሙናም ይሄው አለና›› ለፖሊሱ አስረክቦ ሄደ፡፡
‹‹አቶ ቅጣው ያልሆነ ነገር ለመስራት ፈፅሞ እንዳትሞክር….ይሄው ሳሙና … ሰውነትህን ታጠብና ልብስ ቀይር….››አለው
‹‹ለምን ግን?››ሲል መጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ጠየቀ፡፡
ፖሊሱ እጁ ላይ ያጠለቀለትን ካቴና እየፈታ‹‹ለምን ማለት ..ምኑ?››ሲል ጥያቄው እንዳልገባው በሚገልፅ ሁኔታ መልሶ ጠየቀው፡፡
‹‹መታጠቤና ..ልብስ መቀየሬ?››
‹‹ምነው አሁን ያለህበት ሁኔታ ተመችቶሀል እንዴ?ማጥ ውስጥ ሲንከባለል የከረመ ከርከሮ እኮ ነው የምትመስለው …ለማንኛውም ለምን እንድታጠብ እንደተፈቀደልህ አናውቅም…እኛ የታዘዝነውን እያደረግን ነው…ስራችንን እንድንሰራ ተባበረን..እንካ ልብሱንና ሳሙናውን… ይዘህ ግባ››አለው።
እንዳው በግዴለሽነት ተቀበለውና ወደውስጥ በዝግታ ገብቶ በራፉን ከውስጥ ሊዘጋው ሲል…ፖሊሱ ፈጠን አለና‹‹አይ አትዝጋው…..ክፍት ይሁን …ከእይታችን ውጭ መሆን የለብህም››የሚል ትእዛዝ ሰጠው፡፡
በግዴለሽነት በራፉን መልሶ በልቅጦ ወደውስጥ ገባ…ልብስ የያዘውን ፔስታል በአንዱ የግድግዳው ኮርነር ጋር አስቀምጦ ሳሙናውን ብቻ ይዞ ቀጥታ ሻወር ወደላበት ቦታ ሄደ… ውሀውን እስከመጨረሻ ከፈተውና ውስጡ ቆመ…ውጭ ሆነው በትኩረት እየተከታተሉት ያሉት ሁለት ፖሊሶች በገረሜታ ምን እየሰራነው? ብለው እየተገረሙበት ነበር፡፡ለሀያ ደቂቃ አልተነቃነቀም…ውሀው እየተንፎለፎለ በላዩ ላይ ሲወርድ ከለበሰው ልብስ ላይም ሆነ ከገላው ላይ እየተቀረፈ የሚወርደው ቆሻሻ ለሚያየው ሰው ይዘገንናል..በኋላ ግራ ሲገባቸው አንደኛው ፖሊስ ወደውስጥ ገባና ወደእሱ ተጠግቶ
‹አቶ ቅጣው ..ቅጣው …››ውሀውን ዘጋው ሲል ጠየቀው…ከገባበት ጥልቅ ሰመመን የነቃ የሚመስለው ቅጣው‹‹አቤት በቃ ልውጣ እንዴ?››ሲል ጠየቀ፡፡
‹‹አይ እሱ እስከፈለግክ መታጠብ ትችላለህ..ግን በስርአት አድርገው፡››
‹‹በስርአት ማለት?››ተደነጋገረ፡፡
ሳሙናው እኮ በእጅህ እንደያዝከው ሟሙቶ ሊያልቅ ነው..የለበስከውን ቀፋፊ እና ቡትቶ ልብስ አውጥተህ ጣልና ሰውነትህን ሳሙና እየመታህ በትክክል ታጠብ››
‹‹እ..ገባኝ..እሺ›› ብሎ ልብሶቹን አወላለቀና ከእሱ አርቆ በመወርወር ርቃኑን ቆመና ሻወሩን በድጋሚ ከፈተ…ከዛ ከፀጉሩ በመጀመር ሙሉ ሰውነቱን ሳሙና በመለቅለቅ መታጠብ ጀመረ…ምን አልባትም አምስት ስድስት ጊዜ ደጋግሞ ሳሙና በመለቅለቅ ለወራት በሰውነቱ ተጠቅጥቆ የተከማቸውን ቆሻሻ በተቻለው መልኩ ለማስለቀቅ ጣረ… ከዛ…ቧንቧውን ዘጋና ቀጥታ ወደፔስታሉ በመሄድ ውስጡ ያለውን ልብስ ተራ በተራ እያወጣ በመመልከት ለበሰ…ሁሉም ልብሶች ምርጥና አዲስ ሲሆኑ ለእሱ ግን ሰፍተውታል ….‹‹ምን አልባትም በጣም ከመክሳቴ የተነሳ ለእኔ በልኬ የሚሆን ልብስ ገበያ ላይ ስለሌለ ይሆናል ይሄን ያመጡልኝ››ሲል አሰበና በመጨረሻ ካልሲውንና ጫማውን አድርጎ ወደ ፖሊሶቹ ሄደ….በራፉ ላይ ተቀበሉትና በእጁ ላይ ካቴናውን መልሰው አጠለቁለትና በሌላ አቅጣጫ ይዘውት ሄዱ…አሁንም የወሰዱትን ቦታ ገና እንዳየው ነው ያወቀው›..የእስረኞች ፀጉር ማስተካከያ ቦታ ነው፡፡
‹‹ሽፈራው በል ቆንጆ አድርገህ አስተካክለው››ፖሊሱ ፀጉር አስተካካዩን አዘዘው፡፡
‹‹እንዴ ቅጣው..?እንዴት ነህ..?ሰላም ነህ?››ፀጉር አስተካካዩ በገረሜታ ተቀበለው፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
አዲስ አለም በራሷ መኪና ግን ሹፌር እየነዳላት ከአዳማ ወደአዲስ አበባ እየተጓዘች ነው፡፡
የተቀመጠችው ከኋላ ወንበር ላይ ሲሆን ከግራዋ የራሷ ልጅ ቅዱስ ሲኖር ከግራዋ ደግሞ የፀአዳ ልጅ ምሰር ትገኛለች፡፡
አዲስአለም ወደአዲስ አበባ የምትሄደው እናቷን ለመጠየቅ ነው፡፡ይሄ ቤተሰቦቾ አዳማ ለቀው ወደ አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ በወር ወይም በሁለት ወር አንዴ የምታርገው ነገር ስለሆነ ማንም ለምን እንዴት ብሎ የሚጠይቃት የለም፡፡ምስርን በምን ሰበብ አስፈቅዳ ከእሷ ጋር ይዛት እንደምትመጣ ግን ግራ ገብቷት ነበር፡፡ማታ ነበር ፀአዳ ጋር የደወለች፡፡
‹‹እሺ ጓደኛዬ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰላም ነኝ ምነው ቀን ተገናኝተን ነበር እኮ..በዚህ መሀከል ምን ትሆናለች ብለሽ አሰብሽ?››.
‹‹አንቺ ደግሞ ከአፍሽ ቀና ነገር ቢወጣ ምን አለበት?››
‹‹በይ አሁን ምን ፈልገሽ ነው ወደገደለው ግቢ….››
‹‹በእናትሽ ነገ እነማዬ ጋር አብረን እንሂድ››
‹‹ነገ ››
‹‹አዎ ነገ››
‹‹ያምሻል እንዴ…?ስንት ስራ እንዳለብኝ ስነግርሽ ውዬ እንዴት የማልችለውን ነገር ትጠይቂኛለሽ?››
‹‹ውይ ለካ ስራ አለብሽ..ብቻዬን መሄድ እኮ ደብሮኝ ነው››
ብቻሽን መሄድ ከደበረሽ ታዛዥ እና ጣፋጭ የሆነ ምርጥ ባል አለሽ እሱን አስከትለሽ ሂጂ››
‹‹አንቺ እየሰማሽ እኮ ነው››
‹‹ላውድ ላይ አድርሽ ነው እንዴት የምታወሪኝ… አንቺ እኮ ቅሌታም ነሽ….ለነገሩ ሚኪን በተመለከተ መጥፎ ነገር እንደማልናገር እርግጠኛ ስለሆንኩ እንደፈልገሽ››
‹‹መጥፎ ነገር እንደማትናገሪ እኔም ምስክር ነኝ … ውሸት ግን ትናገሪያለሽ..ምን አልባት እንዳልሺው ጣፋጭ ሊሆን ይችላል ታዛዣ ግን አይደለም..ልክ እንደአንቺው ስራ አለኝ አልችልም የሚል መልስ ነው የሰጠኝ››
‹‹በቃ ከልጅሽ ጋር ሒጂ››
‹‹ወይ እንደውም ተውት ከልጆቼ ጋ ሄዳለው…ምስርን ቆንጆ አድርገሽ አሳምሪያትና ወደስራ ስትሄጂ ይዘሻት ውጭ.. በዛው መጥቼ ወስዳታለው››
‹‹ምን እያልሽ ነው?››ፀአዳ እንደመበሳጨት አለች፡፡
‹‹የራስሽው ምክር እኮ ነው፡፡ልጆቹን ይዤ ሄድና ዘና እንላለን…እናንተም ካለልጆቻችሁ ይድላችሁ…እሁድ ማታ ተመልሰን እንመጣለን፡፡››
‹‹አንቺ እኮ የሆነ መዠገር ነገር ነሽ…እኔ ለራሴ ስንት ስራ አለብኝ..?ገና አሁን እሷን ሰውነቷን ሳጥብ..ፀጉሯን ሰሰራ….››
አላስጨረሰቻትም፡፡‹‹በቃ…ጥዋት ሁለት ተኩል አካባቢ ስራ ቦታሽ እመጣና ወስዳታለው..ደህና እደሪ..እወድሻለው፡፡››ብላት ስልኳን ዘጋችው፡፡እንዳለችውም ጥዋት ስትሄድ ፀአዳ ከነንጭንጯ ልጇን ምስርን አስባና አሳምራ ነበር የጠበቀቻት፡፡
‹‹ውይ ጎደኛዬ ንዴት እንደሸወድኩሽ ስታውቂ እንዴት ትናደጂ ይሆን?›› ብላ አሰበችና ብቻዋን ፈገግ አለች፡፡
ሹፌሩ ጎሮ አካባቢ የሚገኘው የቤተሰቦቾ ቤት ካደረሳት በኃላ ሚካኤል እንዲገዛለት ያዘዘው ዕቃዎች ስለሉ ወደመርካቶ ለመሄድ ተዘጋጀ….
‹‹በቃ ነገ አስር ሰዓት አካባቢ እዚህ ድረስ ››አለችው አዲስ፡፡
‹‹እዚህ የምትንቀሳቀሺበት አይቸግርሽም?››
‹‹ችግር የለውም..የትም የመውጣት እቅድ የለኝም…ምን አልባት የምወጣም ከሆነ ራይድ እጠቀማለው››አለችና ሸኘችው፡፡
ከዛ ልጆቹን ወደቤት አስገብታ እናቷን በቅጡ እንኳን ሰላም ሳትል ነው ወደጓሮ ሄዳ ስልክ የደወለችው፡፡ከሶስት ጥሪ በኃላ ተነሳ‹‹እንዴት ነህ ዘሚካኤል?››
‹‹ሰላም ነኝ..ግን አልተሳካልኝም ብለሽ እንዳታበሳጪኝ››
‹‹አረ ተሳክቶልኛል…መጥተናል እማዬ ቤት ነው ያለነው፡፡››
‹‹በጣም ጎበዝ…..በቃ ጎሮ አካባቢ ነው ያልሺኝ፡፡››
‹‹አዎ… ትክክለኛ አድራሻውን በሚሴጅ ልክልሀለው››
‹‹በቃ..በአንድ ሰዓት ውስጥ እመጣለው››
‹‹ጥሩ ነው..እኛም ገና አሁን መድረሳችን ስለሆነ እስከዛ ከእማዬ ጋ እንጫወታለን…በል ቻው››
‹‹አዲስ በጣም አመሰግናለው…ቻው››
ስልኩ ተዘጋ ፣፣እሷ ግን ፈዛ ቀረች…ከዘሚካኤል ጋር በዚህ መጠን መቀራረብ መቻሏ የተአምር ያህል ነው….ለዘመናት ስታልመውና ስትመኘው የነበረ ነገር ነው፡፡ግን በዚህ መንገድ ይሆናል ብላ ፈፅሞ ሀሳብ አልነበራትም..እሱ የእሷን የልብ ጓደኛ አፍቅሮ እሷ ደግሞ እሱን ከሚያፈቅራት ልጅ ጋር ለማቀራረብ ስትጥር….በራሷ ድርጊት ፈገግ አለች፡፡
‹‹ምን አለበት…. ለሚያፈቅሩት ሰው የሚያፈቅረውን ነገር እዲያገኝ መርዳት ትንሽ ህመም ቢኖረውም ግን ደግሞ ደስ የሚል ስሜት አለው፡፡››አለችና ለስሜቷ ድጋፍ ለመስጠት ሞከረች…የባሏ ሚካኤል ምስል በድንገት መጥቶ አየሩን ሞላው‹‹ፍቅሬ ምን እያሰብሽ ነው…?የገዛ ወንድሜን!!!››ብሎ በሀዘን በተሰበረ ስሜት ሲወቅሳት አየች፡፡
‹‹አንተ ደግሞ ይሄ እኮ ያለፈ ታሪክ ነው….ታውቃለህ እሱን ለማግኘት ስትጥር ነበር ከአንተ ጋር የተቀራረብኩት…ከዛ እሱም ሀገር ጥሎ ጠፋ አንተም ለእኔ ምርጥና ተወዳጅ ሆንክልኝ..እናም በሙሉ ልቤም ወድጄ አገባሁህ››
‹‹ግን ስታገቢኝ…ወደሽ ነው..ወይስ አፍቅረሺኝ?››
‹‹አይ አንተ ደግሞ ምን ቃላት ትመነዝራለህ….ለማንኛውም..የእሱ ያለፈ የአፍላ የወጣትነት ስሜት ነው..አሁን እየቀረብኩትና እየረዳሁት ያለሁት ያንተ ወንድም ስለሆነ ብቻ ነው››
‹‹እንዴ…!!ምንድነው ጓሮ ተደብቀሽ ብቻሽን ምታወሪው?››የእናትዬው የመገረም ንግግር ነበር ከገባችበት ቅዠት መሰል ሀሳብ አባኖ ያወጣት፡፡
‹‹አይ እማዬ ..ምንም አይደል ..የሆነ ነገር እያሰብኩ ነበር››
‹‹የሆነ ነገር..ምነው ከሚካኤል ጋር ተጣላችሁ እንዴ?››
‹‹ወይ እማዬ ምንድነው የምታወሪው..?ከሚካኤል ጋር ለምንድነው የምጣለው?››
‹‹ባልና ሚስት ለምንድነው የሚጣሉት?››
‹‹እኔ እንጃ..እኔና ሚኪ ስንጣለ አይተሸን ታውቂያለሽ?››
‹‹እሱ መልካምና ታጋሽ ባል ስለሆነ ነዋ…እንጂማ እንደአንቺ መመነጫጨቅ ቢሆን… ››እናትዬው ነግግሯን ሳታገባድድ አንጠልጥላ ተወችው፡፡
‹‹እማዬ ደግሞ… የእኔ እናት ነሽ የእሱ?››
‹‹የሁለታችሁም…ባሌ ነው ብለሽ አምጥተሸ ካስተዋወቅሺኝ ቀን ጀምሮ እኮ ልክ እንደአንቺ እሱም ልጄ ሆኗል…በዛ ላይ አሁን ወርቅ የሆነ የልጅ ልጅ ሰጥቶኛል…በይ አሁን ነይ ግቢ ቁርስ ቀርቧል…››አሏትና ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ፡፡
ዘሚካኤል እንዳለውም ከአንድ ሰዓት በኃላ በራፍ ላይ ደርሶ ደወለላቸው፡፡ተዘጋጅታ ስትጠብቀው ስለነበረ ወዲያውኑ ነው ልጆቹን ይዛ የወጣችው፡፡ከግዙፉ ሀመር መኪናው ወርዶ በራፍን ከፍቶ ቆሞ እየጠበቃቸው ነበር…የስድስት አመቷ ምስር እንዳየችው ደነገጠች…..መጀመሪያ የት እንደምታውቀው ነበር ግራ የገባት..ከዛ የምትወደው ዘፋኝና ተዋናይ መሆኑን ስታውቅ ስሜቷን መቆጣጠር አቅቷት እየተንደረደረች ወደ እሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ከቆመበት እጆቹን ዘርግቶ ወደእሷ ተንቀሳቀሰ…እቅፉ ውስጥ ወደቀች.. ጭምቅ አድርጎ አቀፋትና በአየር ላይ አንጠለጠላት..የምስርን ድርጊት ያየው ቅዱስ እጆቹን ከእናቱ እጅ አስለቅቆ ኩስ ኩስ እያለ ምስር እንዳደረገችው ወደዘሚካኤል ሮጠ….አዲስአለም በልጆቹ ያልተጠበቀ ድርጊት በድንጋጤ አፏን ከፈተች ….ሚካኤል ቅዱስ ስሩ ሲደርስ ምስርን ወደአንዱ እጁ አዘዋወራትና ጎንበስ ብሎ ቅዱስን አቅፎ ወደላይ አነሳውና ጉንጮቹን እያገላበጠ ሳመው…..በዚህ ጊዜ አዲስ አለም ከመደነቅ ሳትወጣ ስራቸው ደርሳ ነበር፡፡
‹‹ቆይ ከእነዚህ ልጆች ጋር ከዚህ በፊት ትተዋወቁ ነበር እንዴ?››
ጉንጮቾን እያገላበጠ ሰማት..ትንፋሹ ልክ ሰው ፊት ላይ እደሚበትን አደንዛዥ ዕፅ ኃይል አለው…
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
አዲስ አለም በራሷ መኪና ግን ሹፌር እየነዳላት ከአዳማ ወደአዲስ አበባ እየተጓዘች ነው፡፡
የተቀመጠችው ከኋላ ወንበር ላይ ሲሆን ከግራዋ የራሷ ልጅ ቅዱስ ሲኖር ከግራዋ ደግሞ የፀአዳ ልጅ ምሰር ትገኛለች፡፡
አዲስአለም ወደአዲስ አበባ የምትሄደው እናቷን ለመጠየቅ ነው፡፡ይሄ ቤተሰቦቾ አዳማ ለቀው ወደ አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ በወር ወይም በሁለት ወር አንዴ የምታርገው ነገር ስለሆነ ማንም ለምን እንዴት ብሎ የሚጠይቃት የለም፡፡ምስርን በምን ሰበብ አስፈቅዳ ከእሷ ጋር ይዛት እንደምትመጣ ግን ግራ ገብቷት ነበር፡፡ማታ ነበር ፀአዳ ጋር የደወለች፡፡
‹‹እሺ ጓደኛዬ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰላም ነኝ ምነው ቀን ተገናኝተን ነበር እኮ..በዚህ መሀከል ምን ትሆናለች ብለሽ አሰብሽ?››.
‹‹አንቺ ደግሞ ከአፍሽ ቀና ነገር ቢወጣ ምን አለበት?››
‹‹በይ አሁን ምን ፈልገሽ ነው ወደገደለው ግቢ….››
‹‹በእናትሽ ነገ እነማዬ ጋር አብረን እንሂድ››
‹‹ነገ ››
‹‹አዎ ነገ››
‹‹ያምሻል እንዴ…?ስንት ስራ እንዳለብኝ ስነግርሽ ውዬ እንዴት የማልችለውን ነገር ትጠይቂኛለሽ?››
‹‹ውይ ለካ ስራ አለብሽ..ብቻዬን መሄድ እኮ ደብሮኝ ነው››
ብቻሽን መሄድ ከደበረሽ ታዛዥ እና ጣፋጭ የሆነ ምርጥ ባል አለሽ እሱን አስከትለሽ ሂጂ››
‹‹አንቺ እየሰማሽ እኮ ነው››
‹‹ላውድ ላይ አድርሽ ነው እንዴት የምታወሪኝ… አንቺ እኮ ቅሌታም ነሽ….ለነገሩ ሚኪን በተመለከተ መጥፎ ነገር እንደማልናገር እርግጠኛ ስለሆንኩ እንደፈልገሽ››
‹‹መጥፎ ነገር እንደማትናገሪ እኔም ምስክር ነኝ … ውሸት ግን ትናገሪያለሽ..ምን አልባት እንዳልሺው ጣፋጭ ሊሆን ይችላል ታዛዣ ግን አይደለም..ልክ እንደአንቺው ስራ አለኝ አልችልም የሚል መልስ ነው የሰጠኝ››
‹‹በቃ ከልጅሽ ጋር ሒጂ››
‹‹ወይ እንደውም ተውት ከልጆቼ ጋ ሄዳለው…ምስርን ቆንጆ አድርገሽ አሳምሪያትና ወደስራ ስትሄጂ ይዘሻት ውጭ.. በዛው መጥቼ ወስዳታለው››
‹‹ምን እያልሽ ነው?››ፀአዳ እንደመበሳጨት አለች፡፡
‹‹የራስሽው ምክር እኮ ነው፡፡ልጆቹን ይዤ ሄድና ዘና እንላለን…እናንተም ካለልጆቻችሁ ይድላችሁ…እሁድ ማታ ተመልሰን እንመጣለን፡፡››
‹‹አንቺ እኮ የሆነ መዠገር ነገር ነሽ…እኔ ለራሴ ስንት ስራ አለብኝ..?ገና አሁን እሷን ሰውነቷን ሳጥብ..ፀጉሯን ሰሰራ….››
አላስጨረሰቻትም፡፡‹‹በቃ…ጥዋት ሁለት ተኩል አካባቢ ስራ ቦታሽ እመጣና ወስዳታለው..ደህና እደሪ..እወድሻለው፡፡››ብላት ስልኳን ዘጋችው፡፡እንዳለችውም ጥዋት ስትሄድ ፀአዳ ከነንጭንጯ ልጇን ምስርን አስባና አሳምራ ነበር የጠበቀቻት፡፡
‹‹ውይ ጎደኛዬ ንዴት እንደሸወድኩሽ ስታውቂ እንዴት ትናደጂ ይሆን?›› ብላ አሰበችና ብቻዋን ፈገግ አለች፡፡
ሹፌሩ ጎሮ አካባቢ የሚገኘው የቤተሰቦቾ ቤት ካደረሳት በኃላ ሚካኤል እንዲገዛለት ያዘዘው ዕቃዎች ስለሉ ወደመርካቶ ለመሄድ ተዘጋጀ….
‹‹በቃ ነገ አስር ሰዓት አካባቢ እዚህ ድረስ ››አለችው አዲስ፡፡
‹‹እዚህ የምትንቀሳቀሺበት አይቸግርሽም?››
‹‹ችግር የለውም..የትም የመውጣት እቅድ የለኝም…ምን አልባት የምወጣም ከሆነ ራይድ እጠቀማለው››አለችና ሸኘችው፡፡
ከዛ ልጆቹን ወደቤት አስገብታ እናቷን በቅጡ እንኳን ሰላም ሳትል ነው ወደጓሮ ሄዳ ስልክ የደወለችው፡፡ከሶስት ጥሪ በኃላ ተነሳ‹‹እንዴት ነህ ዘሚካኤል?››
‹‹ሰላም ነኝ..ግን አልተሳካልኝም ብለሽ እንዳታበሳጪኝ››
‹‹አረ ተሳክቶልኛል…መጥተናል እማዬ ቤት ነው ያለነው፡፡››
‹‹በጣም ጎበዝ…..በቃ ጎሮ አካባቢ ነው ያልሺኝ፡፡››
‹‹አዎ… ትክክለኛ አድራሻውን በሚሴጅ ልክልሀለው››
‹‹በቃ..በአንድ ሰዓት ውስጥ እመጣለው››
‹‹ጥሩ ነው..እኛም ገና አሁን መድረሳችን ስለሆነ እስከዛ ከእማዬ ጋ እንጫወታለን…በል ቻው››
‹‹አዲስ በጣም አመሰግናለው…ቻው››
ስልኩ ተዘጋ ፣፣እሷ ግን ፈዛ ቀረች…ከዘሚካኤል ጋር በዚህ መጠን መቀራረብ መቻሏ የተአምር ያህል ነው….ለዘመናት ስታልመውና ስትመኘው የነበረ ነገር ነው፡፡ግን በዚህ መንገድ ይሆናል ብላ ፈፅሞ ሀሳብ አልነበራትም..እሱ የእሷን የልብ ጓደኛ አፍቅሮ እሷ ደግሞ እሱን ከሚያፈቅራት ልጅ ጋር ለማቀራረብ ስትጥር….በራሷ ድርጊት ፈገግ አለች፡፡
‹‹ምን አለበት…. ለሚያፈቅሩት ሰው የሚያፈቅረውን ነገር እዲያገኝ መርዳት ትንሽ ህመም ቢኖረውም ግን ደግሞ ደስ የሚል ስሜት አለው፡፡››አለችና ለስሜቷ ድጋፍ ለመስጠት ሞከረች…የባሏ ሚካኤል ምስል በድንገት መጥቶ አየሩን ሞላው‹‹ፍቅሬ ምን እያሰብሽ ነው…?የገዛ ወንድሜን!!!››ብሎ በሀዘን በተሰበረ ስሜት ሲወቅሳት አየች፡፡
‹‹አንተ ደግሞ ይሄ እኮ ያለፈ ታሪክ ነው….ታውቃለህ እሱን ለማግኘት ስትጥር ነበር ከአንተ ጋር የተቀራረብኩት…ከዛ እሱም ሀገር ጥሎ ጠፋ አንተም ለእኔ ምርጥና ተወዳጅ ሆንክልኝ..እናም በሙሉ ልቤም ወድጄ አገባሁህ››
‹‹ግን ስታገቢኝ…ወደሽ ነው..ወይስ አፍቅረሺኝ?››
‹‹አይ አንተ ደግሞ ምን ቃላት ትመነዝራለህ….ለማንኛውም..የእሱ ያለፈ የአፍላ የወጣትነት ስሜት ነው..አሁን እየቀረብኩትና እየረዳሁት ያለሁት ያንተ ወንድም ስለሆነ ብቻ ነው››
‹‹እንዴ…!!ምንድነው ጓሮ ተደብቀሽ ብቻሽን ምታወሪው?››የእናትዬው የመገረም ንግግር ነበር ከገባችበት ቅዠት መሰል ሀሳብ አባኖ ያወጣት፡፡
‹‹አይ እማዬ ..ምንም አይደል ..የሆነ ነገር እያሰብኩ ነበር››
‹‹የሆነ ነገር..ምነው ከሚካኤል ጋር ተጣላችሁ እንዴ?››
‹‹ወይ እማዬ ምንድነው የምታወሪው..?ከሚካኤል ጋር ለምንድነው የምጣለው?››
‹‹ባልና ሚስት ለምንድነው የሚጣሉት?››
‹‹እኔ እንጃ..እኔና ሚኪ ስንጣለ አይተሸን ታውቂያለሽ?››
‹‹እሱ መልካምና ታጋሽ ባል ስለሆነ ነዋ…እንጂማ እንደአንቺ መመነጫጨቅ ቢሆን… ››እናትዬው ነግግሯን ሳታገባድድ አንጠልጥላ ተወችው፡፡
‹‹እማዬ ደግሞ… የእኔ እናት ነሽ የእሱ?››
‹‹የሁለታችሁም…ባሌ ነው ብለሽ አምጥተሸ ካስተዋወቅሺኝ ቀን ጀምሮ እኮ ልክ እንደአንቺ እሱም ልጄ ሆኗል…በዛ ላይ አሁን ወርቅ የሆነ የልጅ ልጅ ሰጥቶኛል…በይ አሁን ነይ ግቢ ቁርስ ቀርቧል…››አሏትና ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ፡፡
ዘሚካኤል እንዳለውም ከአንድ ሰዓት በኃላ በራፍ ላይ ደርሶ ደወለላቸው፡፡ተዘጋጅታ ስትጠብቀው ስለነበረ ወዲያውኑ ነው ልጆቹን ይዛ የወጣችው፡፡ከግዙፉ ሀመር መኪናው ወርዶ በራፍን ከፍቶ ቆሞ እየጠበቃቸው ነበር…የስድስት አመቷ ምስር እንዳየችው ደነገጠች…..መጀመሪያ የት እንደምታውቀው ነበር ግራ የገባት..ከዛ የምትወደው ዘፋኝና ተዋናይ መሆኑን ስታውቅ ስሜቷን መቆጣጠር አቅቷት እየተንደረደረች ወደ እሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ከቆመበት እጆቹን ዘርግቶ ወደእሷ ተንቀሳቀሰ…እቅፉ ውስጥ ወደቀች.. ጭምቅ አድርጎ አቀፋትና በአየር ላይ አንጠለጠላት..የምስርን ድርጊት ያየው ቅዱስ እጆቹን ከእናቱ እጅ አስለቅቆ ኩስ ኩስ እያለ ምስር እንዳደረገችው ወደዘሚካኤል ሮጠ….አዲስአለም በልጆቹ ያልተጠበቀ ድርጊት በድንጋጤ አፏን ከፈተች ….ሚካኤል ቅዱስ ስሩ ሲደርስ ምስርን ወደአንዱ እጁ አዘዋወራትና ጎንበስ ብሎ ቅዱስን አቅፎ ወደላይ አነሳውና ጉንጮቹን እያገላበጠ ሳመው…..በዚህ ጊዜ አዲስ አለም ከመደነቅ ሳትወጣ ስራቸው ደርሳ ነበር፡፡
‹‹ቆይ ከእነዚህ ልጆች ጋር ከዚህ በፊት ትተዋወቁ ነበር እንዴ?››
ጉንጮቾን እያገላበጠ ሰማት..ትንፋሹ ልክ ሰው ፊት ላይ እደሚበትን አደንዛዥ ዕፅ ኃይል አለው…
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነው፤ የሆነ የሚንጠጣረር ነገር እያደነቆረው ነው፡፡በመከራ ነው ከእንቅልፉ የነቃው…የበራፉ መጥሪያ ድምፅ መሆኑ አወቀ..ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ይላል፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡በዚህ ሰዓት ማን ነው በራፍን መጥሪያ የሚያንጣርረው?፡፡የፅዳት ሰራተኛዋ እንደማትሆን እርግጠኛ ነው፡፡እሷ አንደኛ በዚህ ሰዓት አትመጣም…ብትመጣም የራሷ የሆነ ቁልፍ ስላላት እሱን የምትቀሰቅስበት ምንም አይነት ምክንያት የላትም….መኝታውን ለቆ ተነሳና ጋዎኑን ደርቦ መኝታ ቤቱን ለቆ ወጣ፡፡፡ሳሎን ደርሶ በራፉን ሲከፍት..እየተመለከተ ያለው ፈፅሞ በአእምሮው ያልጠበቀውን ነው፡፡ፊቱን በጥፊ ደረቱን በጡጫ እየቀጠቀጠች ገፍትራ ወደውስጥ አስገብታ ትቦጫጭረው ጀመር….‹‹ምን አድርጌሀለው..?እንዴት በልጄ ስሜት እንደዛ ትጫወታለህ..?ምን አይነት አረመኔ ሰው ብትሆን ነው?፡፡››
እንደዚህ አውሬ የሆነች ሴት በእድሜ ዘመኑ አጋጥሞት አያውቅም፡፡ፊቱን ከብጭሪያ ለመከላከል ሁለቱን እጆቹን በፊቱ ዙሪያ አድርጎ ለመከላከል ሞከረ፡፡
‹‹አረ ፀዲ ተረጋጊ….››
‹‹አልረጋጋም..እንዲህ አሳብደሀኝ እንዴት ነው የምረጋጋው…..?ልጄን እንዴት እንዳሳደኩዋት ታውቃለህ…?››መደባደቧን እና ጮኸቷን አላቆረጠችም….እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኖ እየረገፈ ነው፡፡ትናንት የሆነውን ከሰማችበት ደቂቃ ጀመሮ ማልቀሷን አላቆረጠችም… ለሊቱን እንቅልፍ ባይኗ ሳይዞር ስትቃጠልና ስትነፈርቅ ስላደረች የእናቱን ሞት አዲስ እንደተረዳ ሀዘንተኛ አይኖቾ ከማበጣቸውም በላይ ክፍኛ ደፍርሰዋል፡፡
ዘሚካኤል መከላከሉ ብቻ እንደማያዋጣ ገባው፡፡እንደምንም አለና ሁለት እጆቾን ያዘና ስቦ ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፡፡
‹‹ልቀቀኝ..ከዚህ ቀፋፊ ሰውነትህ ጋር መነካካት …..››አላስጨረሳትም የተከፈተ አፏን በአፉ ከደነው….በተቻላት መጠን ተወራጨች…ከእሱ ፈርጣማና የዳበረ ጡንቻ ማምለጥ አልቻችም…ከንፈሩን ነከሰችው….ለቀቃትና..ተስፈንጥራ ወደኃላ ልታመልጥ ስትል መልሶ በመያዝ ሙሉ በሙሉ ከስር ገብቷ ተሸከማት……እንደእፃን ልጅ በእግሯም በእጇም ተወራጨች… ወደሶፋው ይዟት ሄደ…ሶፋው ላይ ሊወረውረኝ ነው ብላ ስትጠብቅ እሷን አጥብቆ እንደያዘ እግሩን ዘረጋና ከሳፋው ላይ አንዱን ትራስ ወደወለሉ አወረደ….በፍጥነት ገለበጣትና እንደህፃን አቅፎ ወደታች በጉልበቱ ተንበረከከ እና ወለሉ ላይ አስተኛት…ሾልካ ከስሩ ለማምለጥ ታገለች… በጥንካሬ ጨምቆ ከወለሉ ላይ አጣበቃትና ጭንቅላቱን ቀና አድርጎ ትራሱ ላይ አስደገፋት …እንዳይጨፈልቃት በመጠንቀቅ እላዩዋ ላይ ተቀመጠ…የለበሰውን ጋወን አውልቆ ወረወረው….
‹‹ምን ልታደርግ ነው?››አይኗቾ በድንጋጤ ፈጠጡ፡፡
ወደታች ጎንበስ አለና የለበሰችውን ቲሸርት ከግራና ከቀኝ ይዞ ወደታች ተረተረው….የመጨረሻውን ንዴት በመናደዷ ምክንያት ደምስሯ ተግተረተረ‹‹ምን እያደረክ ነው? ልትደፍረኝ ነው እንዴ..?እከስሀለው…ስምህን ነው ያማጠፋው….››የቀራት ብቸኛ መከላከያ ምላሷ ብቻ ነበር….ልታስፈራራው ሞከረች ፡፡ተንጠራራና ሌላ ትራስ አምጥቶ ከጎኗ በማድረግ ከላዬ ላይ ወርዶ ከጓና ተኝቶ ወደራሱ ገለበጣትና አቀፋት፡፡
ከታች እሱ በቁምጣ ሲሆን እሷ ደግሞ ልክ እንደወትሮዋ ጅንስ ሱሪ እንደለበሰች ነው፡፡
‹‹በፈጠሪ ስትበሳጪ እንዴት ነው የምታምሪው?፡፡››
‹‹እያሾፍክብኝ ነው?››
‹‹በፍፅም ..አይገባሽም እንዴ ..?ካንቺ ፍቅር ይዞኛል…ላገባሽ እፈልጋለው››
ምትሰማውን ቃል ማመን አቃታት‹‹ይሄ ደግሞ ሌላ ቀልድ መሆኑ ነው?ሕይወት እንደምትተውነው ተውኔት መሰለህ?››
‹‹እሱ እንዳያያዝሽ ነው …እኔ ግን የተናገርኩት ከልቤ ነው…ከፈለግሽ ዛሬውኑ ሄደን መጋባት እንችላለን…እንደማገባሽ እግጠኛ ስለሆንኩ ነው ምስርን ልጄ ነች ያልኩት፡፡››
‹‹እንዴት እሺ ትለኛልች ብለህ አሳብክ?››
‹‹እንደምትወጂኝ አይኖችሽ ውስጥ ስላነበብኩ››
የተፋቀረ ሁሉ ይጋባል ያለህ ማን ነው….ደግሞ እወቅ እኔ ፍቅር አልፈልግም…አሁን ልቀቀኝ ..ከአንተ እስከወዲያኛው መሸሽና መራቅ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹አይ ከአኔ ሸሽተሸ ማምለጥ አትችይም፡፡››
‹‹ልቀቀኝ አልኩ..›› ለመመናጨቅ ሞከረች አጥብቆ ያዛትና ከንፈሯ ላይ በድጋሚ ተጣበቀ… ሳላሳ ሰከንድ ያህል ብቻ ነው መታገል የቻለችው..ከዛ ቀስ በቀስ እየለዘበች… የእጆቾ ጡንቻዎች እየለሰለሱ ..ከንፈሯቾ ለከንፈሮቹ መልስ እየሰጡ መጡ…እሱን ሲቧጭሩ እና ሲደበድብት የነበሩት ጣቶቹ ጀርባውናና መላ ሰውነቱን ማሻሸት ጀመሩ…ከዛ እሱ ቁምጣውን ሲያወልቅ እሷም በገዛ እጇቾ ጅንስ ሱሪዋን እያወለቀች ነበር….እዛ ግዙፍ የሳሎን ወለል ላይ 30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በፍቅር እየተንከባለሉ እና ከኮርነር ኮርነር እየተሸከረከሩ በጣር የታጅበው ወሲብ ሲሰሩ በራፉ ክፍት መሆኑን እንኳን አላስተዋሉም ነበር፡፡
ከወሲብ በኃላ አርቃኗን ሆና ‹‹አንተ ምን አይነት አዚም ነው ያለህ ግን?››ስትል ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው የፍቅር አዚም ነዋ››
‹‹አይ አይመስለኝም…..የሆነ የሚያደነዝዝ አይነት መስተፋቅርማ አለህ…አሁን ሻወር ቤቱን አሳየኝ..››አለችው፡፡
ከተዘረረበት ወለል እየተነሳ ወደእሷ ሄዶ ከስር ተሸክሞ ወደምኝታ ክፍሉ ተሸክሟት ገባ….‹‹ያው ግቢና ታጠቢ››
‹‹እሺ…ቲሸርቴን ቀዳደሀዋል….አሁን ምን ልለብስ ነው?››እያለች ገባች፡፡
‹‹አታስቢ አዘጋጅልሻለው….ግን አብሬሽ ሻወር መውሰድ እፈልጋለው፡፡››
‹‹ስርአት ይዘህ የምትታጠብ ከሆነ ትችላለህ›› አለችው፡፡በደስታ እርቃኑን ገባና ተቀላቀላት…መታጠብ ጀመሩ፡፡ ቃል እንደገባው ግን ስርዓት ይዞ አልታጠበም..እሷም በቃላት አውጥታ አትናገር እንጂ ስርዓት የለሽ መሆኑን ፈልጋው ነበር..ከዛ ሻወር ቤት ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነበር የወሰደባቸው፡፡ ከዛ ተያይዘው ሲወጡ ሁለቱም ሰውነታቸውን ማዘዝ እስኪያቅታቸው ዝለው ነበር.. ርቃናቸውን ተያይዘው አልጋ ውስጥ ነው የገቡት…ሁለት ሰው መሆናቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተቃቅፈው ለሞት የተቃረበ እንቅልፍ ውስጥ ገቡ፡፡
///
ተመሳሳይ የበራፍ ተደጋግሞ መንጫረር ነበር ከእንቅልፉ ያባነነው..‹‹ዛሬ ደግሞ ምን ጉድ ነው ?››በማለት እየተነጫነጨ…እንደምንም ነቅቶ ስልኩን ሲመለከት..ከ30 በላይ ሚስኮል ነበረው…ሰዓቱን ሲመለከት 7ሰዓት ተኩል ሆኗል…ማመን አልቻለም፡፡ይሄ ሁሉ ሚስኮል ከማን ነው ብሎ ሲያየው አብዛኛው ከአዲስአለም ነው…ስለፀደይ ተጨንቃ እንደሆነ ገመተ ..አልጋውን ለቆ ሲወርድ ፀደይ እራሷን አታውቅም፡፡
ጋወኑን ቅድም ሳሎን ወለል ላይ ትቶት ስለነበረ….ቁምጣ እና ቲሸርት ለበሰና በድኑን እየጎተተ ወደ ሳሎን ሄዶ በራፉን ሲከፍት ክፍኛ የደነገጠችውና አይኗ የፈጠጠው አዲስአለም በራፉ ላይ ተገትራለች
‹‹እዚህ አልመጣችም…?ወይኔ ጓደኛዬ….›
‹‹አረ ተረጋጊ..ግቢ ››
ወደውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘግቶ ተመለሰ‹‹እሺ የት ሄደች ይባላል ?አንተ ደግሞ ለምንድነው ስልክህን የማታነሳው?››
‹‹አሁን ተረጋጊና ከተቻለሽ ቆንጆ ምሳ ስሪልን››
‹‹ምን እያወራህ ነው?ፀደይ ጠፍታለች እኮ ነው የምልህ››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነው፤ የሆነ የሚንጠጣረር ነገር እያደነቆረው ነው፡፡በመከራ ነው ከእንቅልፉ የነቃው…የበራፉ መጥሪያ ድምፅ መሆኑ አወቀ..ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ይላል፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡በዚህ ሰዓት ማን ነው በራፍን መጥሪያ የሚያንጣርረው?፡፡የፅዳት ሰራተኛዋ እንደማትሆን እርግጠኛ ነው፡፡እሷ አንደኛ በዚህ ሰዓት አትመጣም…ብትመጣም የራሷ የሆነ ቁልፍ ስላላት እሱን የምትቀሰቅስበት ምንም አይነት ምክንያት የላትም….መኝታውን ለቆ ተነሳና ጋዎኑን ደርቦ መኝታ ቤቱን ለቆ ወጣ፡፡፡ሳሎን ደርሶ በራፉን ሲከፍት..እየተመለከተ ያለው ፈፅሞ በአእምሮው ያልጠበቀውን ነው፡፡ፊቱን በጥፊ ደረቱን በጡጫ እየቀጠቀጠች ገፍትራ ወደውስጥ አስገብታ ትቦጫጭረው ጀመር….‹‹ምን አድርጌሀለው..?እንዴት በልጄ ስሜት እንደዛ ትጫወታለህ..?ምን አይነት አረመኔ ሰው ብትሆን ነው?፡፡››
እንደዚህ አውሬ የሆነች ሴት በእድሜ ዘመኑ አጋጥሞት አያውቅም፡፡ፊቱን ከብጭሪያ ለመከላከል ሁለቱን እጆቹን በፊቱ ዙሪያ አድርጎ ለመከላከል ሞከረ፡፡
‹‹አረ ፀዲ ተረጋጊ….››
‹‹አልረጋጋም..እንዲህ አሳብደሀኝ እንዴት ነው የምረጋጋው…..?ልጄን እንዴት እንዳሳደኩዋት ታውቃለህ…?››መደባደቧን እና ጮኸቷን አላቆረጠችም….እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኖ እየረገፈ ነው፡፡ትናንት የሆነውን ከሰማችበት ደቂቃ ጀመሮ ማልቀሷን አላቆረጠችም… ለሊቱን እንቅልፍ ባይኗ ሳይዞር ስትቃጠልና ስትነፈርቅ ስላደረች የእናቱን ሞት አዲስ እንደተረዳ ሀዘንተኛ አይኖቾ ከማበጣቸውም በላይ ክፍኛ ደፍርሰዋል፡፡
ዘሚካኤል መከላከሉ ብቻ እንደማያዋጣ ገባው፡፡እንደምንም አለና ሁለት እጆቾን ያዘና ስቦ ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፡፡
‹‹ልቀቀኝ..ከዚህ ቀፋፊ ሰውነትህ ጋር መነካካት …..››አላስጨረሳትም የተከፈተ አፏን በአፉ ከደነው….በተቻላት መጠን ተወራጨች…ከእሱ ፈርጣማና የዳበረ ጡንቻ ማምለጥ አልቻችም…ከንፈሩን ነከሰችው….ለቀቃትና..ተስፈንጥራ ወደኃላ ልታመልጥ ስትል መልሶ በመያዝ ሙሉ በሙሉ ከስር ገብቷ ተሸከማት……እንደእፃን ልጅ በእግሯም በእጇም ተወራጨች… ወደሶፋው ይዟት ሄደ…ሶፋው ላይ ሊወረውረኝ ነው ብላ ስትጠብቅ እሷን አጥብቆ እንደያዘ እግሩን ዘረጋና ከሳፋው ላይ አንዱን ትራስ ወደወለሉ አወረደ….በፍጥነት ገለበጣትና እንደህፃን አቅፎ ወደታች በጉልበቱ ተንበረከከ እና ወለሉ ላይ አስተኛት…ሾልካ ከስሩ ለማምለጥ ታገለች… በጥንካሬ ጨምቆ ከወለሉ ላይ አጣበቃትና ጭንቅላቱን ቀና አድርጎ ትራሱ ላይ አስደገፋት …እንዳይጨፈልቃት በመጠንቀቅ እላዩዋ ላይ ተቀመጠ…የለበሰውን ጋወን አውልቆ ወረወረው….
‹‹ምን ልታደርግ ነው?››አይኗቾ በድንጋጤ ፈጠጡ፡፡
ወደታች ጎንበስ አለና የለበሰችውን ቲሸርት ከግራና ከቀኝ ይዞ ወደታች ተረተረው….የመጨረሻውን ንዴት በመናደዷ ምክንያት ደምስሯ ተግተረተረ‹‹ምን እያደረክ ነው? ልትደፍረኝ ነው እንዴ..?እከስሀለው…ስምህን ነው ያማጠፋው….››የቀራት ብቸኛ መከላከያ ምላሷ ብቻ ነበር….ልታስፈራራው ሞከረች ፡፡ተንጠራራና ሌላ ትራስ አምጥቶ ከጎኗ በማድረግ ከላዬ ላይ ወርዶ ከጓና ተኝቶ ወደራሱ ገለበጣትና አቀፋት፡፡
ከታች እሱ በቁምጣ ሲሆን እሷ ደግሞ ልክ እንደወትሮዋ ጅንስ ሱሪ እንደለበሰች ነው፡፡
‹‹በፈጠሪ ስትበሳጪ እንዴት ነው የምታምሪው?፡፡››
‹‹እያሾፍክብኝ ነው?››
‹‹በፍፅም ..አይገባሽም እንዴ ..?ካንቺ ፍቅር ይዞኛል…ላገባሽ እፈልጋለው››
ምትሰማውን ቃል ማመን አቃታት‹‹ይሄ ደግሞ ሌላ ቀልድ መሆኑ ነው?ሕይወት እንደምትተውነው ተውኔት መሰለህ?››
‹‹እሱ እንዳያያዝሽ ነው …እኔ ግን የተናገርኩት ከልቤ ነው…ከፈለግሽ ዛሬውኑ ሄደን መጋባት እንችላለን…እንደማገባሽ እግጠኛ ስለሆንኩ ነው ምስርን ልጄ ነች ያልኩት፡፡››
‹‹እንዴት እሺ ትለኛልች ብለህ አሳብክ?››
‹‹እንደምትወጂኝ አይኖችሽ ውስጥ ስላነበብኩ››
የተፋቀረ ሁሉ ይጋባል ያለህ ማን ነው….ደግሞ እወቅ እኔ ፍቅር አልፈልግም…አሁን ልቀቀኝ ..ከአንተ እስከወዲያኛው መሸሽና መራቅ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹አይ ከአኔ ሸሽተሸ ማምለጥ አትችይም፡፡››
‹‹ልቀቀኝ አልኩ..›› ለመመናጨቅ ሞከረች አጥብቆ ያዛትና ከንፈሯ ላይ በድጋሚ ተጣበቀ… ሳላሳ ሰከንድ ያህል ብቻ ነው መታገል የቻለችው..ከዛ ቀስ በቀስ እየለዘበች… የእጆቾ ጡንቻዎች እየለሰለሱ ..ከንፈሯቾ ለከንፈሮቹ መልስ እየሰጡ መጡ…እሱን ሲቧጭሩ እና ሲደበድብት የነበሩት ጣቶቹ ጀርባውናና መላ ሰውነቱን ማሻሸት ጀመሩ…ከዛ እሱ ቁምጣውን ሲያወልቅ እሷም በገዛ እጇቾ ጅንስ ሱሪዋን እያወለቀች ነበር….እዛ ግዙፍ የሳሎን ወለል ላይ 30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በፍቅር እየተንከባለሉ እና ከኮርነር ኮርነር እየተሸከረከሩ በጣር የታጅበው ወሲብ ሲሰሩ በራፉ ክፍት መሆኑን እንኳን አላስተዋሉም ነበር፡፡
ከወሲብ በኃላ አርቃኗን ሆና ‹‹አንተ ምን አይነት አዚም ነው ያለህ ግን?››ስትል ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው የፍቅር አዚም ነዋ››
‹‹አይ አይመስለኝም…..የሆነ የሚያደነዝዝ አይነት መስተፋቅርማ አለህ…አሁን ሻወር ቤቱን አሳየኝ..››አለችው፡፡
ከተዘረረበት ወለል እየተነሳ ወደእሷ ሄዶ ከስር ተሸክሞ ወደምኝታ ክፍሉ ተሸክሟት ገባ….‹‹ያው ግቢና ታጠቢ››
‹‹እሺ…ቲሸርቴን ቀዳደሀዋል….አሁን ምን ልለብስ ነው?››እያለች ገባች፡፡
‹‹አታስቢ አዘጋጅልሻለው….ግን አብሬሽ ሻወር መውሰድ እፈልጋለው፡፡››
‹‹ስርአት ይዘህ የምትታጠብ ከሆነ ትችላለህ›› አለችው፡፡በደስታ እርቃኑን ገባና ተቀላቀላት…መታጠብ ጀመሩ፡፡ ቃል እንደገባው ግን ስርዓት ይዞ አልታጠበም..እሷም በቃላት አውጥታ አትናገር እንጂ ስርዓት የለሽ መሆኑን ፈልጋው ነበር..ከዛ ሻወር ቤት ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነበር የወሰደባቸው፡፡ ከዛ ተያይዘው ሲወጡ ሁለቱም ሰውነታቸውን ማዘዝ እስኪያቅታቸው ዝለው ነበር.. ርቃናቸውን ተያይዘው አልጋ ውስጥ ነው የገቡት…ሁለት ሰው መሆናቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተቃቅፈው ለሞት የተቃረበ እንቅልፍ ውስጥ ገቡ፡፡
///
ተመሳሳይ የበራፍ ተደጋግሞ መንጫረር ነበር ከእንቅልፉ ያባነነው..‹‹ዛሬ ደግሞ ምን ጉድ ነው ?››በማለት እየተነጫነጨ…እንደምንም ነቅቶ ስልኩን ሲመለከት..ከ30 በላይ ሚስኮል ነበረው…ሰዓቱን ሲመለከት 7ሰዓት ተኩል ሆኗል…ማመን አልቻለም፡፡ይሄ ሁሉ ሚስኮል ከማን ነው ብሎ ሲያየው አብዛኛው ከአዲስአለም ነው…ስለፀደይ ተጨንቃ እንደሆነ ገመተ ..አልጋውን ለቆ ሲወርድ ፀደይ እራሷን አታውቅም፡፡
ጋወኑን ቅድም ሳሎን ወለል ላይ ትቶት ስለነበረ….ቁምጣ እና ቲሸርት ለበሰና በድኑን እየጎተተ ወደ ሳሎን ሄዶ በራፉን ሲከፍት ክፍኛ የደነገጠችውና አይኗ የፈጠጠው አዲስአለም በራፉ ላይ ተገትራለች
‹‹እዚህ አልመጣችም…?ወይኔ ጓደኛዬ….›
‹‹አረ ተረጋጊ..ግቢ ››
ወደውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘግቶ ተመለሰ‹‹እሺ የት ሄደች ይባላል ?አንተ ደግሞ ለምንድነው ስልክህን የማታነሳው?››
‹‹አሁን ተረጋጊና ከተቻለሽ ቆንጆ ምሳ ስሪልን››
‹‹ምን እያወራህ ነው?ፀደይ ጠፍታለች እኮ ነው የምልህ››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
/////
እሱም ጃኬቱን ይዞ ተከተላት፡፡እራሱ እያሸከረከረ የምትፈልገው መስሪያ ቤት ድረስ ወሰዳት፡፡
‹‹እ…ትጠብቀኛለህ ወይስ ትሄዳለህ?››
‹‹ኸረ በፍፁም.. አብሬሸ እገባለው››
‹‹ተው እዚሁ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ..ከአንተ ጋር የሆነ ቦታ መሄድ እኳ በሴቶች አይን ክፉኛ መገረፍ ነው..ታውቃለህ የሰው አይን ደግሞ ያቃጥላል፡፡››
‹‹አረ ባክሽ…!!!››ሞተሩን አጠፋና ከመኪናው ወረዳ… እሷም ወረደች…ክንዷን ያዘና ወደውስጥ መራመድ ጀመረ..መራመድ አቅቷት እግሯቾ ተሳሰሩባት፡፡ግን ምርጫ አልነበራትም፡፡
ግቢ ውስጥ ገቡና ወደኢንፎሪሜሽን ዴስክ ሲደርሱ እሱን እንግዳ ማረፊያ ወንበር ላይ አስቀጠችውና እሷ ወደዛው አመራች…ከአስር ደቀቂቃ በኃላ ግን አንገቷን ደፍታ ወደእሱ ተመለሰችና ከጎኑ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ምነው ፍቅር…አገኘሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ ..ጠመሙብኝ …ሰውዬው ከአራት አመት በፊት የዚህ ቢሮ ዳሬክተር ዴሬክቶሬት ነበረ…አሁን የት እንዳለና ቢያንስ ስልኩን እንዲሰጡኝ ነበር የጠየቅኳቸው…››
‹‹ቆይ ሰውዬው ምንሽ ነው?››
‹‹ምኔም አይደለም..ጭራሽም አላውቀውም..ግን ስለአባቴ መረጃ እንዳለው በሆነ መንገድ አውቄለው…እሱን ካገኘው አባቴ ይሙት ይኑር ማወቅ እችላለው፡፡››
የነገረችውን ያለምንም ጥርጣሬ አመናት…አሳዘነችው፡፡‹‹የሰውዬው ስም ማን ነው?››
ሙሉ ስሙን ነገረችው፡፡
‹‹ቆይ እንደውም ተነሽ›› ብሎ እጇን ይዞ ወደኢንፎርሜሽን ዴስኩ መራመድ ጀመረ..እሷ ምን ሊያደርግ እንደሆነ ሳይገባት ዝም ብላ ተጎተተችለት፡፡እንደደረሰ በትንሿ መስኮት ጎንበስ ብሎ ሲመለከት ..ሁለት ልጅ እግር ሴቶች ታዩት
‹‹ጤና ይስጥልኝ?›› ሲላቸው ሁለቱም አፋቸውን ከፍተው ፀጥ አሉት፡፡
‹‹እባካችሁ የሆነ ነገር ላስቸግራችሁ ነበር››
‹‹ምን ፈለክ…?ምን እንርዳህ?››አንደኛዋ ከመቀመጫዋ ተነስታ በመንሰፍሰፍ ጠየቀችው፡፡
‹‹እሷ እህቴ ነች..ከኃላው ያለችውን ፀአዳን ተመለከተችና‹‹ማንን ነበር ያልሽን?››ስትል ድጋሚ ጠየቀቻት፡፡
ፀአዳ ነገረቻት፡፡‹‹ቆይ እስኪ ››አለችና በኋላው በራፍ በመውጣት ወደእነሱ መጣች..እስቲ ተከተሉኝ ጋሽ ይርጋ በደንብ ያውቃሉ፡፡ጋሽ ይርጋ ማለት እዚህ መስሪያ ቤት ለ30አመት የሰሩ የመዝገብት ቤት ሰራተኛ ናቸው፡፡››የምታወራውን እያዳመጡ ከኋላ ተከተሏት‹‹አስቸገርን አይደል..?››አላት፡፡
ወደኃላ ዞራ‹‹‹አረ ችግር የለውም…ለዛውም ላንተ..ባይ ዘወዌ በጣም አድናቂህ ነኝ››አለችው
‹‹አመሰግናለው››ትህትና ባልተለየው የድምፅ ቃና መለሰላት፡፡
ከ10 ደቂቃ በኃላ የሰውየውን ሙሉ አድራሻ ይዘው ከቢሮ ወጡ…መኪና ውስጥ ገብተው መጓዝ እንደጀመሩን‹‹አየሽ አንቺን ሰምቼ ከስርሽ ቀርቼ ቢሆን ኖረ ምን እንደሚያጋጥምሽ ተመልከቺ››አላት በኩራት፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..አድራሻውን እንዲህ በቀላሉ አላገኘውም ነበር›
‹‹እና ሽልማት የለኝም?››
‹‹አለህ..ምን ትፈልገለህ…?መክሰስ ልጋብዝህ?››
‹‹አዎ ግን ቤትሽ››
‹‹ቤትሽ?››ግራ በመጋባት አፍጥጣ አየችው፡፡
‹‹አዎ ምነው ላደርስሽ አይደል…አሁን አስር ተኩልነው… አስራሁለት ሰዓት ሳይሆን እዛ እንደርሳለን…ከዛ ቤትሽ መክሰስ ትጋብዢኛለሽ››
‹‹ለምን መክሰስ..እራት ቢሆንልህ አይሻልም….በዛውም ታድራለህ››
በፈገግታ ተሞልቶ‹‹አንቺ እኮ ምርጥ ነሽ…….››ሲል መለሰ
‹‹አረ አላደርገውም …..ጎረቤቶቼስ ምን ይሉኛል.?.››
‹‹ምንም ይበሉሽ……››
‹‹አይ አይቻልም ከፈለክ ውጭ ልጋብዝህ››
‹‹ውጭ አልፍግም….. ባይሆን እዛ እስክንደርስ አስቢበት››አላት፡
ቀጥታ ወደአዳማ እየነዳ ነው፡፡‹‹አሁን ታዲያ እንዴት ልታደርጊ ነው?››
‹‹ግራ ገብቶኛል..ግን ምን ቢሆን ነው አንድ አመት ሙሉ አማኑኤል ህክምና ላይ የቆየው››
‹‹ያው አማኑኤል ምን ሲኮን ነው የሚቆየው? ጭንቅላቱን አሟት ነዋ….፡፡››መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ከዛ ሲወጣ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ቤተሰቦቹ ጋር ቦንጋ እንደገባ ነው የነገሩን ..እንዴት እንደዛ አይነት ውሳኔ ወሰነ…?ይታይህ በአንድ ወቅት ትልቅ ስልጣን ላይ የነበረ ጉምቱ ባለስልጣን በዛ ላይ ዶ/ር ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ቦንጋ …ከቦንጋም ገጠር ጠቅልሎ ሲገባ አይገርምም፡፡
‹‹ይገርማል..ግን እደእኔ እንደእኔ የብልህ ውሳኔ ነው የወሰነው ..ይሄ ሰው ጭንቀትና የአእምሮ በሽታ ካለበት ትክክለኛ መረጋጊያ ቦታ ገጠር ነው..ይታይሽ እዚህ አዲስ አበባ እንኳን ለአእመሮ ህመምተኛ ለጤነኛው ሰው ትርምሱና ኳኳታው አስጨናቂ ነው…ይልቅ እኔ ያሳሰበኝ ….አሁን ምን ልታደርጊ ነው?፡፡የሚለው ነው፡፡
‹‹ቦታው ላይ ሄጄ እድሌን ሞክራለው››ስትል በእርግጠኝነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእውነት ?››አለ ደነግጦ፡፡
‹‹አዎ….ይሄ እኮ ሲሪዬስ ነገር ነው….››
‹‹አውቃለው ..ግን እዛ ደረስ ሄደሽ ምንም ሊነግርሽ ባይችልስ…..?ማለቴ ከጤናው አንፃር ምንም ነገር ባያስታውስስ?››
‹‹ምንም ይሁን ምን ሰውዬውን ፊት ለፊት አግኝቼው መሞከር እፈልጋለው….ካለበለዚያ,--እረፍት አላገኝም፡፡››ስትል መለሰችለት፡፡
///
አቶ ቅጣው አዲሱ ክፍሉ በጣም ተመችቶታል…እንደውም በፊት ካለበት ክፍል ጋር ሲነፃፀር ከሲኦል ወደገነት የመዘዋወር አይነት ነው፡፡መኝታ አልጋ ያለው ..በቂ ብርሀን የሚያስገባ ንፁህ ክፍል ነው ያስገቡት፡፡በዛ ላይ እግሩም ሆነ እጁ ከሰንሰለት እስር ነፃ ስለሆነና ምግብም ሰዓቱን ጠብቆ ስለሚመጣለት ሰውነቱ ተአምራዊ በሆነ መልኩ እያገገመ ነው፡፡ክፍል ውስጥም ቢሆን እንደፈለገው እየተንቀሳቀሰ ቀላል ስፖርቶችን መስራት ችሏል…በዛ ምክንያት መንፈሱም ሆነ አካሉ ልዩ ለውጥ አምጥቷል፡፡
አሁን ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቁዱስ እያነበበ ነው፡፡ይሄንን መፅሀፍ ቅዱስ ከ10 ቀን በፊት ነበር ጠያቂው እና መካሪው መነኩሴ ናቸው አምጥተው የሰጡት፡፡ወዲያው ግን ማንበብ አልቻለም ነበር…፡፡አይኖቹ ለወራት ጨለማ ክፍል ውስጥ ስለከረሙ በቀላሉ ከብዣታ አገግመው ፊደል እየለቀሙ ለማንበብ ተቸግረው ነበር…ከጥቂት ቀናት ወደዚህ ግን እንደምንም ለማንበብ ችሏል፡፡
መለኩሴው የመጡ ቀን እንደተለመደው..ጠያቂ አለህ ተብሎ ነበር ከክፍል የተወሰደው፡፡የሚጠብቁት ክፍል ውስጥ ሲገባ እንደወትሮ በሰንሰለት እጅና እግሮቹ ተጠፍሮ የተቀደደ እና የተቦጫጨቀ ልብስ ለብሶ ሳይሆን በተለየ ሁኔታ ነበር፡፡እና በዚህ ሁኔታ ይደነቃሉ ብሎ ጠብቆ የነበረ ቢሆንም መነኩሴው ግን ልክ እንደወትሮ በተመሳሳይ ስሜት ነበር ያተናገሩት
ልጄ ይህ ግንኙነታችን የመጨረሻችን ነው… ልሰናበትህ ነው የመጣውት..›› ሲሉት ከዚ በፊት ተሰምቶት የማያውቀው ብቸኝነት ነው የተሰማው፡፡
‹‹አባ ለምን…?መመላለሱን ሰለቹ እንዴ?››
‹‹አይደለም… ልጄ ልሄድ ነው››
‹‹ወዴት ነው የሚሄዱት?››
‹‹ወደአባቴ…ወደፈጣሪ››
ሌላ ድንጋጤ፣‹‹እንዴ ያሞታል እንዴ?››
ፈገግ አሉ‹‹ አይ ልጄ ወደፈጣሪ ለመሄድ እኮ የግድ መታመም የለብንም…አምላክ በቃ ወደእኔ ና ብሎኛል…የዛሬዋን የመጨረሻ ቀኔ አንተንና ሌሎች ልጆቼን ለመሰናብት ነው የሰጠኝ..መቼስ ፡እሱ ለቸርነቱ ዳርቻ የለው… እኔ ሀጥያተኛውን መሞቻ ቀኔን ነገሮች ለመሰናበቻ ሚሆን ቀን ፈቅዶልኝ…ተመስገን ነው ..ተመስገን፡፡››
መነኩሴው የሚያወሩትን ሊገባው አልቻለም፡፡‹‹አባ እኔ ሞት የተፈረደብኝ ሰው እያለው እርሶ…..››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
/////
እሱም ጃኬቱን ይዞ ተከተላት፡፡እራሱ እያሸከረከረ የምትፈልገው መስሪያ ቤት ድረስ ወሰዳት፡፡
‹‹እ…ትጠብቀኛለህ ወይስ ትሄዳለህ?››
‹‹ኸረ በፍፁም.. አብሬሸ እገባለው››
‹‹ተው እዚሁ መኪና ውስጥ ጠብቀኝ..ከአንተ ጋር የሆነ ቦታ መሄድ እኳ በሴቶች አይን ክፉኛ መገረፍ ነው..ታውቃለህ የሰው አይን ደግሞ ያቃጥላል፡፡››
‹‹አረ ባክሽ…!!!››ሞተሩን አጠፋና ከመኪናው ወረዳ… እሷም ወረደች…ክንዷን ያዘና ወደውስጥ መራመድ ጀመረ..መራመድ አቅቷት እግሯቾ ተሳሰሩባት፡፡ግን ምርጫ አልነበራትም፡፡
ግቢ ውስጥ ገቡና ወደኢንፎሪሜሽን ዴስክ ሲደርሱ እሱን እንግዳ ማረፊያ ወንበር ላይ አስቀጠችውና እሷ ወደዛው አመራች…ከአስር ደቀቂቃ በኃላ ግን አንገቷን ደፍታ ወደእሱ ተመለሰችና ከጎኑ ቁጭ አለች፡፡
‹‹ምነው ፍቅር…አገኘሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ ..ጠመሙብኝ …ሰውዬው ከአራት አመት በፊት የዚህ ቢሮ ዳሬክተር ዴሬክቶሬት ነበረ…አሁን የት እንዳለና ቢያንስ ስልኩን እንዲሰጡኝ ነበር የጠየቅኳቸው…››
‹‹ቆይ ሰውዬው ምንሽ ነው?››
‹‹ምኔም አይደለም..ጭራሽም አላውቀውም..ግን ስለአባቴ መረጃ እንዳለው በሆነ መንገድ አውቄለው…እሱን ካገኘው አባቴ ይሙት ይኑር ማወቅ እችላለው፡፡››
የነገረችውን ያለምንም ጥርጣሬ አመናት…አሳዘነችው፡፡‹‹የሰውዬው ስም ማን ነው?››
ሙሉ ስሙን ነገረችው፡፡
‹‹ቆይ እንደውም ተነሽ›› ብሎ እጇን ይዞ ወደኢንፎርሜሽን ዴስኩ መራመድ ጀመረ..እሷ ምን ሊያደርግ እንደሆነ ሳይገባት ዝም ብላ ተጎተተችለት፡፡እንደደረሰ በትንሿ መስኮት ጎንበስ ብሎ ሲመለከት ..ሁለት ልጅ እግር ሴቶች ታዩት
‹‹ጤና ይስጥልኝ?›› ሲላቸው ሁለቱም አፋቸውን ከፍተው ፀጥ አሉት፡፡
‹‹እባካችሁ የሆነ ነገር ላስቸግራችሁ ነበር››
‹‹ምን ፈለክ…?ምን እንርዳህ?››አንደኛዋ ከመቀመጫዋ ተነስታ በመንሰፍሰፍ ጠየቀችው፡፡
‹‹እሷ እህቴ ነች..ከኃላው ያለችውን ፀአዳን ተመለከተችና‹‹ማንን ነበር ያልሽን?››ስትል ድጋሚ ጠየቀቻት፡፡
ፀአዳ ነገረቻት፡፡‹‹ቆይ እስኪ ››አለችና በኋላው በራፍ በመውጣት ወደእነሱ መጣች..እስቲ ተከተሉኝ ጋሽ ይርጋ በደንብ ያውቃሉ፡፡ጋሽ ይርጋ ማለት እዚህ መስሪያ ቤት ለ30አመት የሰሩ የመዝገብት ቤት ሰራተኛ ናቸው፡፡››የምታወራውን እያዳመጡ ከኋላ ተከተሏት‹‹አስቸገርን አይደል..?››አላት፡፡
ወደኃላ ዞራ‹‹‹አረ ችግር የለውም…ለዛውም ላንተ..ባይ ዘወዌ በጣም አድናቂህ ነኝ››አለችው
‹‹አመሰግናለው››ትህትና ባልተለየው የድምፅ ቃና መለሰላት፡፡
ከ10 ደቂቃ በኃላ የሰውየውን ሙሉ አድራሻ ይዘው ከቢሮ ወጡ…መኪና ውስጥ ገብተው መጓዝ እንደጀመሩን‹‹አየሽ አንቺን ሰምቼ ከስርሽ ቀርቼ ቢሆን ኖረ ምን እንደሚያጋጥምሽ ተመልከቺ››አላት በኩራት፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..አድራሻውን እንዲህ በቀላሉ አላገኘውም ነበር›
‹‹እና ሽልማት የለኝም?››
‹‹አለህ..ምን ትፈልገለህ…?መክሰስ ልጋብዝህ?››
‹‹አዎ ግን ቤትሽ››
‹‹ቤትሽ?››ግራ በመጋባት አፍጥጣ አየችው፡፡
‹‹አዎ ምነው ላደርስሽ አይደል…አሁን አስር ተኩልነው… አስራሁለት ሰዓት ሳይሆን እዛ እንደርሳለን…ከዛ ቤትሽ መክሰስ ትጋብዢኛለሽ››
‹‹ለምን መክሰስ..እራት ቢሆንልህ አይሻልም….በዛውም ታድራለህ››
በፈገግታ ተሞልቶ‹‹አንቺ እኮ ምርጥ ነሽ…….››ሲል መለሰ
‹‹አረ አላደርገውም …..ጎረቤቶቼስ ምን ይሉኛል.?.››
‹‹ምንም ይበሉሽ……››
‹‹አይ አይቻልም ከፈለክ ውጭ ልጋብዝህ››
‹‹ውጭ አልፍግም….. ባይሆን እዛ እስክንደርስ አስቢበት››አላት፡
ቀጥታ ወደአዳማ እየነዳ ነው፡፡‹‹አሁን ታዲያ እንዴት ልታደርጊ ነው?››
‹‹ግራ ገብቶኛል..ግን ምን ቢሆን ነው አንድ አመት ሙሉ አማኑኤል ህክምና ላይ የቆየው››
‹‹ያው አማኑኤል ምን ሲኮን ነው የሚቆየው? ጭንቅላቱን አሟት ነዋ….፡፡››መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ከዛ ሲወጣ ሁሉን ነገር ጣጥሎ ቤተሰቦቹ ጋር ቦንጋ እንደገባ ነው የነገሩን ..እንዴት እንደዛ አይነት ውሳኔ ወሰነ…?ይታይህ በአንድ ወቅት ትልቅ ስልጣን ላይ የነበረ ጉምቱ ባለስልጣን በዛ ላይ ዶ/ር ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ቦንጋ …ከቦንጋም ገጠር ጠቅልሎ ሲገባ አይገርምም፡፡
‹‹ይገርማል..ግን እደእኔ እንደእኔ የብልህ ውሳኔ ነው የወሰነው ..ይሄ ሰው ጭንቀትና የአእምሮ በሽታ ካለበት ትክክለኛ መረጋጊያ ቦታ ገጠር ነው..ይታይሽ እዚህ አዲስ አበባ እንኳን ለአእመሮ ህመምተኛ ለጤነኛው ሰው ትርምሱና ኳኳታው አስጨናቂ ነው…ይልቅ እኔ ያሳሰበኝ ….አሁን ምን ልታደርጊ ነው?፡፡የሚለው ነው፡፡
‹‹ቦታው ላይ ሄጄ እድሌን ሞክራለው››ስትል በእርግጠኝነት መለሰችለት፡፡
‹‹የእውነት ?››አለ ደነግጦ፡፡
‹‹አዎ….ይሄ እኮ ሲሪዬስ ነገር ነው….››
‹‹አውቃለው ..ግን እዛ ደረስ ሄደሽ ምንም ሊነግርሽ ባይችልስ…..?ማለቴ ከጤናው አንፃር ምንም ነገር ባያስታውስስ?››
‹‹ምንም ይሁን ምን ሰውዬውን ፊት ለፊት አግኝቼው መሞከር እፈልጋለው….ካለበለዚያ,--እረፍት አላገኝም፡፡››ስትል መለሰችለት፡፡
///
አቶ ቅጣው አዲሱ ክፍሉ በጣም ተመችቶታል…እንደውም በፊት ካለበት ክፍል ጋር ሲነፃፀር ከሲኦል ወደገነት የመዘዋወር አይነት ነው፡፡መኝታ አልጋ ያለው ..በቂ ብርሀን የሚያስገባ ንፁህ ክፍል ነው ያስገቡት፡፡በዛ ላይ እግሩም ሆነ እጁ ከሰንሰለት እስር ነፃ ስለሆነና ምግብም ሰዓቱን ጠብቆ ስለሚመጣለት ሰውነቱ ተአምራዊ በሆነ መልኩ እያገገመ ነው፡፡ክፍል ውስጥም ቢሆን እንደፈለገው እየተንቀሳቀሰ ቀላል ስፖርቶችን መስራት ችሏል…በዛ ምክንያት መንፈሱም ሆነ አካሉ ልዩ ለውጥ አምጥቷል፡፡
አሁን ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ቁዱስ እያነበበ ነው፡፡ይሄንን መፅሀፍ ቅዱስ ከ10 ቀን በፊት ነበር ጠያቂው እና መካሪው መነኩሴ ናቸው አምጥተው የሰጡት፡፡ወዲያው ግን ማንበብ አልቻለም ነበር…፡፡አይኖቹ ለወራት ጨለማ ክፍል ውስጥ ስለከረሙ በቀላሉ ከብዣታ አገግመው ፊደል እየለቀሙ ለማንበብ ተቸግረው ነበር…ከጥቂት ቀናት ወደዚህ ግን እንደምንም ለማንበብ ችሏል፡፡
መለኩሴው የመጡ ቀን እንደተለመደው..ጠያቂ አለህ ተብሎ ነበር ከክፍል የተወሰደው፡፡የሚጠብቁት ክፍል ውስጥ ሲገባ እንደወትሮ በሰንሰለት እጅና እግሮቹ ተጠፍሮ የተቀደደ እና የተቦጫጨቀ ልብስ ለብሶ ሳይሆን በተለየ ሁኔታ ነበር፡፡እና በዚህ ሁኔታ ይደነቃሉ ብሎ ጠብቆ የነበረ ቢሆንም መነኩሴው ግን ልክ እንደወትሮ በተመሳሳይ ስሜት ነበር ያተናገሩት
ልጄ ይህ ግንኙነታችን የመጨረሻችን ነው… ልሰናበትህ ነው የመጣውት..›› ሲሉት ከዚ በፊት ተሰምቶት የማያውቀው ብቸኝነት ነው የተሰማው፡፡
‹‹አባ ለምን…?መመላለሱን ሰለቹ እንዴ?››
‹‹አይደለም… ልጄ ልሄድ ነው››
‹‹ወዴት ነው የሚሄዱት?››
‹‹ወደአባቴ…ወደፈጣሪ››
ሌላ ድንጋጤ፣‹‹እንዴ ያሞታል እንዴ?››
ፈገግ አሉ‹‹ አይ ልጄ ወደፈጣሪ ለመሄድ እኮ የግድ መታመም የለብንም…አምላክ በቃ ወደእኔ ና ብሎኛል…የዛሬዋን የመጨረሻ ቀኔ አንተንና ሌሎች ልጆቼን ለመሰናብት ነው የሰጠኝ..መቼስ ፡እሱ ለቸርነቱ ዳርቻ የለው… እኔ ሀጥያተኛውን መሞቻ ቀኔን ነገሮች ለመሰናበቻ ሚሆን ቀን ፈቅዶልኝ…ተመስገን ነው ..ተመስገን፡፡››
መነኩሴው የሚያወሩትን ሊገባው አልቻለም፡፡‹‹አባ እኔ ሞት የተፈረደብኝ ሰው እያለው እርሶ…..››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ዴርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይና ዘሚካኤል ዶ/ሩን ለማግኘት ቦንጋ ከተማ ይገኛሉ፡፡ይሄ ጉዞ እንደዚህ አልነበረም የታሰበው፡፡ሚካኤልና እሷ ነበሩ ለሳምንታት አብረው ለመሄድ ሲዘጋጁ የነበሩት፡፡ከዛ ዝግጅቱ ሁሉ ተጠናቆ…ሚካኤል ቻርተር አውሮፕላን ተከራይቶ ወደቦንጋ ለመብረር ከአዳማ ተነስተው አውሮፕላኑ ወደሚገኝበት አዲስ አበባ ሲደርሱ ዘሚካኤል ጠበቃቸው፡፡
ሁለቱም ያልጠቁት ነገር ስለሆነ በጣም ነበር ግራ የተጋቡት፡፡ዘሚካኤል እንደአጋጣሚ ከአዲስአለም ጋር ሲደዋወል ነበር ስለጉዞው የነገረችው፡፡
ለማናቸውም ሰላምታ ሳይሰጥ‹‹ፀዲ ከእኔ ጋር ነው መሄድ ያለብሽ?››አላት፡፡
‹‹ማለት…?ለምን ሲባል?››
‹‹በቃ ካንቺ ጋር መሄድና አብሬሽ መሆን እፈልጋለው››
ሚካኤል እጁን አጣጥፎ በገረሜታ እና በትዝብት እየተከታተላቸው ነው፡፡ፀደይን በተመለከተ እንዲህ ሲሪዬስ በመሆኑ ደስታ ተሰምቶታል፡፡
‹‹አይ…ከሚኪ ጋር ነው የምንሄደው…..አንተን ማስቸገር አልፈልግም››ኮስተር ብላ ተቃወመችው፡፡
እሱም ከእሷ በጠነከረ መኮሳተር‹‹እኔ ደግሞ አልስማማም….በችግርሽ ጊዜ አብሬሽ መሆን እፈልጋለው….የአባትሽን አድራሻ ብታገኚም ባታገኚም አብሬሽ ሆኜ ደስታሽንም ሆነ ሀዘንሽን መካፈል አለብኝ››ብሎ ግግም አለ፡፡
ሚካኤል ፀአዳ ስለ/ዶሩ እንደዋሸችው ስለሚያውቅ በውስጡ ፈገግ እያለ‹‹ፀዲ አንዴ ላናግርሽ?››አላት፡፡
‹‹ቆይ ጠብቀኝ መጣው››ብላው ከዘሚካኤል ተለየችና ወደሚካኤል ሄደች፡፡
‹‹ፀዲ እሱ አንዴ ከጠመመ እሺ አይልም..››አላት፡፡
‹‹እና ከእሱ ጋር ሄጄ እንዴት ልሆን ነው?››
‹‹አሪፍ ነው እንደውም…ይሄ የእግዚያብሄር የራሱ እቅድ ይሆናል…ሁኔታዎችን እንዳመጣጣቸው ትወጫቸዋለሽ… ከሰውዬው የሆነ ጠቃሚ መረጃ ብናገኝ እንኳን እሱን አስረድቶ ማሳመን ከባድ ነው የሚሆንብን .. በኃላ እንዲህ ነው የተፈጠረው..እንደዛ ነው የሆነው ከምንል ቀጥታ ከፈረሱ አፍ ቢሰማ ነው የሚሻለው››
‹‹አረ ተው ሚኪ..››
‹‹ግድ የለሽም ባንቺ እተማመንብሻለው፡፡››አለና ጉንጮን ስሞ በፈገግታ በመጣበት መኪና ተመልሶ ሄደ፡፡
///
እንግዲህ በዚህ ሁኔታ ነው ሁለቱ ቦንጋ ከተማ ሊገኙ የቻሉት፡፡እንደደረሱ ፀደይ ከዘሚካኤል ዞር አለችን የዶ/ሩ ነው ተብሎ በተሰጣት ስልክ ደውላ ነበር፡፡የዶ/ር ወንድም ነኝ የሚል ሰው ነበር አንስቶ ያዋራት፡፡‹‹ለምን እንደመጣችና ዶ/ርን ለምን ጉዳይ እንደፈለገችው በአጭሩ ነገረችው፡፡
‹‹ላናግረውና መልሼ ልደውልልሽ ››አለና ስልኩን ዘጋ፡፡ሰውዬው መልሶ እስኪደውል ለሀያ ደቂቃ ተጨንቃ ነበር፡፡‹‹አይ ማግኘት አልፈልግም ቢል ምን አደርጋለው?››የሚልው ሀሳብ ትንፋሽ እስኪያጥራት ድረስ ነበር ያስጨነቃት፡፡ደውሎ ግን አስደሳች ነገር ነው የነገራት፡፡ በፈለጉት ሰዓት መምጣት እንደሚችሉ እና ሊያናግራቸው ፍቃደኛ እንደሆነ ነገራት፡፡ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያው ነበር ባጀጃጅ በመከራየት ከከተማው የአንድ ሰዓት መንገድ ወደሚርቅ ገጠር ጉዞ ጀመሩ፡፡
እየሄዱ ሳሉ በገጠሩ ውበት ተደምማ..ዶዶላ ሆኜ አልፎ እልፎ ገጠር ሄድ ነበር..እዛም እንዲህ ውብ ነበር….እና በጣም ነበር ደስተኛ የምሆነው፡፡››
‹‹ገጠር ዘመድ ነበረሽ?››
‹‹አይ የጎደኛዬ ቤተሰቦች ገጠር ነበሩ.. እሱ ነበር ይዞኝ የሚሄደው››
‹‹ጓደኛዬ ስትይ…?››
‹‹የምስር አባት››
ወደራሱ ጎትቶ እያቀፋት‹‹በጣም ነው አይደል የጎዳሽ?››አላት ፡፡
‹‹አዎ!!በፊት በጣም የምጠላውና ባገኘው የምገድለው ይመስለኝ ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ?››
‹‹…አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ይቅር ብዬዋለው››አለችው፡፡
‹‹ግን እንዴት በዛ መጠን የምትጠይውን ሰው እንዲህ በቀላሉ ይቅር ማለት ቻልሽ?››ሲል በገረሜታ ጠየቃት፡፡ይህንን ጥያቄ የጠየቃት እሱ በቤተሰቦቹ ላይ የቋጠረውን ቂምና ጥላቻ አሁንም በልቡ ውስጥ ቋጥኝ ሆኖ እያስጨነቀው በመሆኑ እሷ የነገረችውን ነገር ማመን ስላቃተው ነው፡፡
እሷ ግን እርግጠኛ በመሆን ታስረዳው ጀመር….‹‹ምን መሰለህ..በእኔና በእሱ መካከል የተፈጠረው ችገር የዛሬ ስድስት አመት የሆነ ነው››
‹‹እና ጊዜ ቁስልን ይፈውሳል በሚለው ብሂል ሄደሽ ነው?››
‹‹አይ እንደእሱ አይደለም…ሳስበው የዛሬ ስድስት አመት የነበረችው ፀደይ አሁን ካለችው ፀደይ ጋር በብዙ ነገር እንደምትለይ ገባኝ..እንደውም አንዳንዴ ያቺ ፀደይ ልክ እንደአንድ የምወዳት ዘመዴ ትናፍቀኛለች…››
እያወራች ያለችው መጀመሪያ ከተነሱበት ሀሳብ ጋር ምንም አልገጣጠም አለው…ቢሆንም በትግስት ማደመጡን ለመቀጠል ወሰነ..
እሷም ቀጠለች‹‹እና አሁን ያለሁት ፀደይ የዛን ጊዜ ባለፍኩበት ሁኔታ ላይ ብሆን ተመሳሳይ ችግር ላይ እወድቃለው..?ብወድቅስ ተመሳሳይ ምላሽ ነው የምሰጠው..?ማለቴ ራሴን ስለማጥፋት አስባለው….?ቤተሰቦቼንና ሀገሬን ጥዬ ወደማላውቀው ከተማ እሰደዳለው…?አንዱንም አላደርግም…፡፡ችግሩን በተለየ መንገድ ነበር የምፈታው…ይሄንን ወደ እሱ ቀየርኩት…አሁን እሱ በህይወት ካለ የሆነች ሴት አፍቅሮ ካስረገዘ በኃላ ደምፁ አጥፍቶ ይሸሻል…?እርግጠኛ ነኝ ቢያንስ እናትዬውን እንኳን ለማግባት ባይፈልግ ልጁን የራስሽ ጉዳይ ብሎ ዞር አይልም፡፡ታዲያ ዛሬ ባገኘውና ጥላቻዬን ባሳውቀው ካዛም አልፌ ልበቀለው ብሞክር ትርጉም ይሰጣል…አይሰጥም..፡፡ምክንያቱም ያ እኔ ማውቀው ልጅ ጠፍቶል… በብዙ ነገር ተቀይሮ በብዙ መከራ ውስጥ አልፎ ብዙ ህይወት ልምዶችን ቀስሞ ሌላ ሰው ሆኖ ነው ማገኘው..እና ሌላ ሰው ባጠፋው ሌላ ሰው የመቅጣት ያህል ነው….ለዛ ነው ይቅር ልለው የወሰንኩት፡፡››
ዘሚካኤል ዝም ነው ያላት…የነገረችውን ጠቅላላ ወደራሱ ህይወት ወስዶ ነው ማሰላሰል የፈለገው…፡፡ከዛሬ ሰባት በፊት የነበረው ዘሚካኤልና አሁን ካለው ዘሚካኤል ፈፅሞ የማይመሳሰል… የተለያየ ፍላጎት ..የተለየ አላማና አመለካከት ያለው ነው ፡፡እና መቶ ፐርሰንት የሚመሳሰሉበት ነገር ቢኖር በስማቸው ነው፡፡እሱንም ቢሆን የአባቱን ስም ስላስቀየረ….መቶ ፐርሰንት ሊባል አይችልም፡፡
//
ከቦንጋ ከተማ የአንድሰዓት እግር መንገድ ሄደው ነው ሰውዬውን ያገኙት፡፡ግዙፉ የሆነ በአረንጎዴ ዛፎችና ተክሎች ተሞላ ውብ ግቢ ነው የገቡት፡፡የሰውዬው ወንድም ነው የተቀበላቸው፡፡ ‹‹ወደማሳ ሄዶል አሁን መምጫው ደርሶል ግቡና ጠብቁት ››ብሎ ወደግዙፉ የሳር ጎጆ ቤት ይዞቸው ገባ ፡፡ቤቱ ፅድት ያለ ነው፡፡ጥግ ላይ በለአንድ ሜትር የተነጠፈ አልጋ አለ..ከአልጋው አጠገብ ከእንጨት የተሰራ መደርደሪያ አለ..መደርደሪያው ግማሽ በመፅሀፍ ተሞልቷል፡፡ከስር በኩል አንድ መለስተኛ ቴፕ ይታያል፡፡
‹‹ግቡ ››አላቸውን የሚቀመጡበት ወንበር ሰጣቸው፡፡እና መቀመጣቸውን ካረጋገጠ በኃላ ተመልሶ ወጣ፡፡
‹‹አይ ሰውዬው ጥሩ ሁኔታ ላይ ሳይሆን አይቀርም››አላት ዘሚካኤል፡፡
‹‹በምን አወቅክ?››
‹‹አንድ ሰውን እኮ በቤቱ ሁኔታ መገመት ትቺያለሽ..አታይም እንዴ ምንም የቆሸሸ ምንም የትዝረከረከ ነገር የለም….››
‹‹እንደአፍህ ያድርግልኝ.››አለችው፡፡
ድንገት ዘሚካኤል ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ ተነሳ..ሁኔታው ፀአዳን በጣም አስደነገጣት…እና አብራው ብድግ አለች…የሆነ እባብ ያየ ነው የመሰላት….ተንዳርድሮ ወደአልጋው ተጠጋ ..ከአልጋው በግራ በኩል ባለ መለስተኛ ጠረጴዛ ላይ ብዛት ያላቸው በፍሬም ያሉ ፎቶዎች ተደርድረውበታል…ቀጥታ ሔደና ተራ በተራ እያነሳ ያያቸው ጀመር….ፀደይ ያልጠበቀችው ነገር ነው ያጋጠማት…ፎቶውን እያየ ወደእሷ ዞረና አፈጠጠባት›
‹‹ይሄ ምንድነው?››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ዴርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይና ዘሚካኤል ዶ/ሩን ለማግኘት ቦንጋ ከተማ ይገኛሉ፡፡ይሄ ጉዞ እንደዚህ አልነበረም የታሰበው፡፡ሚካኤልና እሷ ነበሩ ለሳምንታት አብረው ለመሄድ ሲዘጋጁ የነበሩት፡፡ከዛ ዝግጅቱ ሁሉ ተጠናቆ…ሚካኤል ቻርተር አውሮፕላን ተከራይቶ ወደቦንጋ ለመብረር ከአዳማ ተነስተው አውሮፕላኑ ወደሚገኝበት አዲስ አበባ ሲደርሱ ዘሚካኤል ጠበቃቸው፡፡
ሁለቱም ያልጠቁት ነገር ስለሆነ በጣም ነበር ግራ የተጋቡት፡፡ዘሚካኤል እንደአጋጣሚ ከአዲስአለም ጋር ሲደዋወል ነበር ስለጉዞው የነገረችው፡፡
ለማናቸውም ሰላምታ ሳይሰጥ‹‹ፀዲ ከእኔ ጋር ነው መሄድ ያለብሽ?››አላት፡፡
‹‹ማለት…?ለምን ሲባል?››
‹‹በቃ ካንቺ ጋር መሄድና አብሬሽ መሆን እፈልጋለው››
ሚካኤል እጁን አጣጥፎ በገረሜታ እና በትዝብት እየተከታተላቸው ነው፡፡ፀደይን በተመለከተ እንዲህ ሲሪዬስ በመሆኑ ደስታ ተሰምቶታል፡፡
‹‹አይ…ከሚኪ ጋር ነው የምንሄደው…..አንተን ማስቸገር አልፈልግም››ኮስተር ብላ ተቃወመችው፡፡
እሱም ከእሷ በጠነከረ መኮሳተር‹‹እኔ ደግሞ አልስማማም….በችግርሽ ጊዜ አብሬሽ መሆን እፈልጋለው….የአባትሽን አድራሻ ብታገኚም ባታገኚም አብሬሽ ሆኜ ደስታሽንም ሆነ ሀዘንሽን መካፈል አለብኝ››ብሎ ግግም አለ፡፡
ሚካኤል ፀአዳ ስለ/ዶሩ እንደዋሸችው ስለሚያውቅ በውስጡ ፈገግ እያለ‹‹ፀዲ አንዴ ላናግርሽ?››አላት፡፡
‹‹ቆይ ጠብቀኝ መጣው››ብላው ከዘሚካኤል ተለየችና ወደሚካኤል ሄደች፡፡
‹‹ፀዲ እሱ አንዴ ከጠመመ እሺ አይልም..››አላት፡፡
‹‹እና ከእሱ ጋር ሄጄ እንዴት ልሆን ነው?››
‹‹አሪፍ ነው እንደውም…ይሄ የእግዚያብሄር የራሱ እቅድ ይሆናል…ሁኔታዎችን እንዳመጣጣቸው ትወጫቸዋለሽ… ከሰውዬው የሆነ ጠቃሚ መረጃ ብናገኝ እንኳን እሱን አስረድቶ ማሳመን ከባድ ነው የሚሆንብን .. በኃላ እንዲህ ነው የተፈጠረው..እንደዛ ነው የሆነው ከምንል ቀጥታ ከፈረሱ አፍ ቢሰማ ነው የሚሻለው››
‹‹አረ ተው ሚኪ..››
‹‹ግድ የለሽም ባንቺ እተማመንብሻለው፡፡››አለና ጉንጮን ስሞ በፈገግታ በመጣበት መኪና ተመልሶ ሄደ፡፡
///
እንግዲህ በዚህ ሁኔታ ነው ሁለቱ ቦንጋ ከተማ ሊገኙ የቻሉት፡፡እንደደረሱ ፀደይ ከዘሚካኤል ዞር አለችን የዶ/ሩ ነው ተብሎ በተሰጣት ስልክ ደውላ ነበር፡፡የዶ/ር ወንድም ነኝ የሚል ሰው ነበር አንስቶ ያዋራት፡፡‹‹ለምን እንደመጣችና ዶ/ርን ለምን ጉዳይ እንደፈለገችው በአጭሩ ነገረችው፡፡
‹‹ላናግረውና መልሼ ልደውልልሽ ››አለና ስልኩን ዘጋ፡፡ሰውዬው መልሶ እስኪደውል ለሀያ ደቂቃ ተጨንቃ ነበር፡፡‹‹አይ ማግኘት አልፈልግም ቢል ምን አደርጋለው?››የሚልው ሀሳብ ትንፋሽ እስኪያጥራት ድረስ ነበር ያስጨነቃት፡፡ደውሎ ግን አስደሳች ነገር ነው የነገራት፡፡ በፈለጉት ሰዓት መምጣት እንደሚችሉ እና ሊያናግራቸው ፍቃደኛ እንደሆነ ነገራት፡፡ጊዜ ሳያባክኑ ወዲያው ነበር ባጀጃጅ በመከራየት ከከተማው የአንድ ሰዓት መንገድ ወደሚርቅ ገጠር ጉዞ ጀመሩ፡፡
እየሄዱ ሳሉ በገጠሩ ውበት ተደምማ..ዶዶላ ሆኜ አልፎ እልፎ ገጠር ሄድ ነበር..እዛም እንዲህ ውብ ነበር….እና በጣም ነበር ደስተኛ የምሆነው፡፡››
‹‹ገጠር ዘመድ ነበረሽ?››
‹‹አይ የጎደኛዬ ቤተሰቦች ገጠር ነበሩ.. እሱ ነበር ይዞኝ የሚሄደው››
‹‹ጓደኛዬ ስትይ…?››
‹‹የምስር አባት››
ወደራሱ ጎትቶ እያቀፋት‹‹በጣም ነው አይደል የጎዳሽ?››አላት ፡፡
‹‹አዎ!!በፊት በጣም የምጠላውና ባገኘው የምገድለው ይመስለኝ ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ?››
‹‹…አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ይቅር ብዬዋለው››አለችው፡፡
‹‹ግን እንዴት በዛ መጠን የምትጠይውን ሰው እንዲህ በቀላሉ ይቅር ማለት ቻልሽ?››ሲል በገረሜታ ጠየቃት፡፡ይህንን ጥያቄ የጠየቃት እሱ በቤተሰቦቹ ላይ የቋጠረውን ቂምና ጥላቻ አሁንም በልቡ ውስጥ ቋጥኝ ሆኖ እያስጨነቀው በመሆኑ እሷ የነገረችውን ነገር ማመን ስላቃተው ነው፡፡
እሷ ግን እርግጠኛ በመሆን ታስረዳው ጀመር….‹‹ምን መሰለህ..በእኔና በእሱ መካከል የተፈጠረው ችገር የዛሬ ስድስት አመት የሆነ ነው››
‹‹እና ጊዜ ቁስልን ይፈውሳል በሚለው ብሂል ሄደሽ ነው?››
‹‹አይ እንደእሱ አይደለም…ሳስበው የዛሬ ስድስት አመት የነበረችው ፀደይ አሁን ካለችው ፀደይ ጋር በብዙ ነገር እንደምትለይ ገባኝ..እንደውም አንዳንዴ ያቺ ፀደይ ልክ እንደአንድ የምወዳት ዘመዴ ትናፍቀኛለች…››
እያወራች ያለችው መጀመሪያ ከተነሱበት ሀሳብ ጋር ምንም አልገጣጠም አለው…ቢሆንም በትግስት ማደመጡን ለመቀጠል ወሰነ..
እሷም ቀጠለች‹‹እና አሁን ያለሁት ፀደይ የዛን ጊዜ ባለፍኩበት ሁኔታ ላይ ብሆን ተመሳሳይ ችግር ላይ እወድቃለው..?ብወድቅስ ተመሳሳይ ምላሽ ነው የምሰጠው..?ማለቴ ራሴን ስለማጥፋት አስባለው….?ቤተሰቦቼንና ሀገሬን ጥዬ ወደማላውቀው ከተማ እሰደዳለው…?አንዱንም አላደርግም…፡፡ችግሩን በተለየ መንገድ ነበር የምፈታው…ይሄንን ወደ እሱ ቀየርኩት…አሁን እሱ በህይወት ካለ የሆነች ሴት አፍቅሮ ካስረገዘ በኃላ ደምፁ አጥፍቶ ይሸሻል…?እርግጠኛ ነኝ ቢያንስ እናትዬውን እንኳን ለማግባት ባይፈልግ ልጁን የራስሽ ጉዳይ ብሎ ዞር አይልም፡፡ታዲያ ዛሬ ባገኘውና ጥላቻዬን ባሳውቀው ካዛም አልፌ ልበቀለው ብሞክር ትርጉም ይሰጣል…አይሰጥም..፡፡ምክንያቱም ያ እኔ ማውቀው ልጅ ጠፍቶል… በብዙ ነገር ተቀይሮ በብዙ መከራ ውስጥ አልፎ ብዙ ህይወት ልምዶችን ቀስሞ ሌላ ሰው ሆኖ ነው ማገኘው..እና ሌላ ሰው ባጠፋው ሌላ ሰው የመቅጣት ያህል ነው….ለዛ ነው ይቅር ልለው የወሰንኩት፡፡››
ዘሚካኤል ዝም ነው ያላት…የነገረችውን ጠቅላላ ወደራሱ ህይወት ወስዶ ነው ማሰላሰል የፈለገው…፡፡ከዛሬ ሰባት በፊት የነበረው ዘሚካኤልና አሁን ካለው ዘሚካኤል ፈፅሞ የማይመሳሰል… የተለያየ ፍላጎት ..የተለየ አላማና አመለካከት ያለው ነው ፡፡እና መቶ ፐርሰንት የሚመሳሰሉበት ነገር ቢኖር በስማቸው ነው፡፡እሱንም ቢሆን የአባቱን ስም ስላስቀየረ….መቶ ፐርሰንት ሊባል አይችልም፡፡
//
ከቦንጋ ከተማ የአንድሰዓት እግር መንገድ ሄደው ነው ሰውዬውን ያገኙት፡፡ግዙፉ የሆነ በአረንጎዴ ዛፎችና ተክሎች ተሞላ ውብ ግቢ ነው የገቡት፡፡የሰውዬው ወንድም ነው የተቀበላቸው፡፡ ‹‹ወደማሳ ሄዶል አሁን መምጫው ደርሶል ግቡና ጠብቁት ››ብሎ ወደግዙፉ የሳር ጎጆ ቤት ይዞቸው ገባ ፡፡ቤቱ ፅድት ያለ ነው፡፡ጥግ ላይ በለአንድ ሜትር የተነጠፈ አልጋ አለ..ከአልጋው አጠገብ ከእንጨት የተሰራ መደርደሪያ አለ..መደርደሪያው ግማሽ በመፅሀፍ ተሞልቷል፡፡ከስር በኩል አንድ መለስተኛ ቴፕ ይታያል፡፡
‹‹ግቡ ››አላቸውን የሚቀመጡበት ወንበር ሰጣቸው፡፡እና መቀመጣቸውን ካረጋገጠ በኃላ ተመልሶ ወጣ፡፡
‹‹አይ ሰውዬው ጥሩ ሁኔታ ላይ ሳይሆን አይቀርም››አላት ዘሚካኤል፡፡
‹‹በምን አወቅክ?››
‹‹አንድ ሰውን እኮ በቤቱ ሁኔታ መገመት ትቺያለሽ..አታይም እንዴ ምንም የቆሸሸ ምንም የትዝረከረከ ነገር የለም….››
‹‹እንደአፍህ ያድርግልኝ.››አለችው፡፡
ድንገት ዘሚካኤል ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ ተነሳ..ሁኔታው ፀአዳን በጣም አስደነገጣት…እና አብራው ብድግ አለች…የሆነ እባብ ያየ ነው የመሰላት….ተንዳርድሮ ወደአልጋው ተጠጋ ..ከአልጋው በግራ በኩል ባለ መለስተኛ ጠረጴዛ ላይ ብዛት ያላቸው በፍሬም ያሉ ፎቶዎች ተደርድረውበታል…ቀጥታ ሔደና ተራ በተራ እያነሳ ያያቸው ጀመር….ፀደይ ያልጠበቀችው ነገር ነው ያጋጠማት…ፎቶውን እያየ ወደእሷ ዞረና አፈጠጠባት›
‹‹ይሄ ምንድነው?››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ዘሚካኤል እንግዳው ላይ አፍጥጦ
‹‹አይ ምንም እየገባኝ አይደለም….?››አለ
ሰውዬውም ዘሚካኤል‹‹ቁጭ በል አስረዳሀለው..››አለና ወደውስጥ ገብቶ ቀድሞ ተቀመጠ…
ፀደይ ዘሚካኤልን እየጎተተች ይዛው መጣችና አስቀመጠችው…እሷም ተቀመጠችን ስልኳን አውጥታ ሪከርድ ላይ አደረገችና ሰውዬው የሚናገረውን ለመስማት ዝግጁ ሆነች፡፡
‹‹ምን ድረስ ታውቃላችሁ?››
‹‹እኔ ምንም የማውቀው ነገር የለም››ዘሚካኤል በትግስተ የለሽነት መለሰ፡፡
ፀደይ ዝም አለች‹‹ጥሩ ከመጀመሪያው ብጀምርላችሁ ችግር የለውም..እኔ እና እናትህ የልጅነት ጓደኛሞች ማለት ፍቅረኛሞች ነበርን…በጣም ነበር የምንዋደደው…..ምንጊዜም ስለመጋባትና ዕድሜ ዘመናችንን ሙሉ አብሮ ስለመኖር ነበር የምናስበው…ከዛ ድንገት አባቴ ወደአሜሪካ መሄድ አለብህ አለኝ…ብዙ ወንድሞቹ እዛ ስላሉ ሀሳቡን ላስቀይረው አልቻልኩም….አባቴን በጣም ነበር የምፈራው..ከዛ ጥያቄውን ተቀብዬ ወደአሜሪካ ሄድኩ…ለካ እሷ በወቅቱ እህትህን ፀንሳ ነበር..፡፡››
‹‹ፀንሳ ማለት …ከማን?››
‹‹ከማን ይሆናል ከእኔ ነዋ››
‹‹እና እህቴ የአንተ ልጅ ነች…?.ምንድነው የምትቀባጥረው?››
‹‹አልቀባጠርኩም..ከፈለክ አባትህን ጠይቀው …ያውቃል…እናትህ እኔ ጥያት ስለሄድኩ በጣም ተበሳጭታብኝ ስለነበር እና በዛ ላይ አርግዛ ስለነበር…ወዲያው አባትህን አገባችው…ስታገባው..ለልጇ አባት ለማግኘት አንጂ አፍቅራው አልነበረም…እሱም ይወዳት ስለነበረ ተንከባከባት….እህትህም በሰባት ወር እንደተወለደች ነበር ያሰበው…የገዛ ልጁ ነበር የምትመስለው….ስለዚህ ትርሲትን እንደልጁ አሳደጋት..ከዛ አንተ እና ወንድምህ ተወለዳችሁ፡፡እኔም ከሀያ አመት ቆይታ በኃላ ከአሜሪካ ተመለስኩ፡፡ለእሷ የነበረኝ ፍቅር ከውስጤ ስላልበረደ ፈልጌ አገኘኋት…በጣም ተበሳጭታብኝ የነበረ ቢሆንም ታፈቅረኝ ስለነበረ በሂደት ይቅር አለቺኝ…አባትህን ፈታ እኔን እንድተገባኝ እጨቀጭቃት ጀመር…እሷም ምንም እንኳን ከእኔ ጋር ለመጋባት በጣም ፍላጎት ቢኖራትም እናንተን መበተን ስላልፈለገች በሀሳቤ ልትስማማ አልቻለችም፡፡
እኔም እሷን ትቼ ሌላ ሴት ማግባት ብሞክርም አልቻልኩም..አቃተኝ…ከዛ በቃ አንቺ እሺ ብለሽ ባልሽን ፈተሸ ማታገቢኝ ከሆነ ቢያንስ ልጄን የማግኘት መብት አለኝ..ለልጄ አባቷ እኔ እንደሆንኩ ንገሪያት እያልኩ በዚህ መጨቃጨቅ ጀመርን፡፡እሷም ያንን ማድረግ አልችልም እያለች መከላከል ጀመረች፡፡በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን በድብቅ እየተገናኘን ፍቅራችንን እንወጣ ነበር…
‹‹ለምን ያህል ጊዜ ከአባቴ እየተደበቃችሁ ..እንደዛ አደረጋችሁ?››ግሽግሽ ባለና ጥላቻ በተጫነው ስሜት ጠየቀው፡፡
‹‹አራት ወይም አምስት አመት››መለሰለት
‹‹እና አባቴ ይሄን ሁሉ ታሪክ ሲያውቅ ነዋ ..ቀልቡን ነስቶት ያንን ወንጀል የፈፀመው?››
‹‹አይ አይደለም…ስለዚህ ጉዳይ ሳስብ እስከዛሬ ድረስ ራሴን መቆጣጠር እስኪያቅተኝ አዝናለው..እመነኝ በጉዳዩ በጣም መፀፀት ብቻ ሳይሆን ብዙ ነገሬን አጥቼበታለው….፡፡ ስራዬን፤ ጤናዬን …ብዙ ብዙ ነገር…ብዙ ጊዜም ራሴን አጥፍቼ ከልጄ ትርሲት እና ከእናትህ ጎን ለመተኛት ሞክሬ ነበር..ግን በሆነ መንገድ እተርፋለው…መጨረሻ ይሄው እንደምታየኝ የአያቴ መንደር መጥቼ በዚህ አይነት ሁኔታ መኖር ጀመርኩ..ትንሽም ወደእዚህ ከመጣሁ ነው ጤነኛ የሆንኩት››
‹‹ሰውዬ እኔ ያንተን ፀፀት ለመስማተ ምንም አይነት ፍላጎት የለኝም..ስለዋናው ጉዳይ ንገረኝ››
‹‹ትዝ ይለኛል ቀኑ እሁድ ነበር….በእለቱ አባትህ ሞጆ የጓደኛው ለቅሶ ስለነበረ መሄዱን እናትህ ስትነግረኝ..መኪናዬን ከአዲስአበባ አስነስቼ አዳማ ሄድኩ ፡፡እናትህን ተቀጣጥረን ስለነበር ቡቲክ አገኘኋት …እሁድ በዛ ላይ ጥዋት ስለሆነ የገበያ ግር ግር አልነበረም.. ከዛ የተወሰነ ከቆየን በኃላ የተለመደ ጭቅጭቃችንን ጀመርን‹‹ …ለልጄ አባቷ መሆኔን ወይ ቀድመሽ ንገሪያት ወይ እነግራታለው››አልኳት፡፡
‹‹እሷ ቅጣውን በልዩ ሁኔታ ነው የምትወደው …አባትሽ ቅጣው አይደለም ብላት ልጄ በጣም ነው ምትጎዳው››አለቺኝ፡፡
‹‹ብትጎዳም ለጊዜው ነው…ከውሸት ጋር ለዘላለም ከምትኖር እውነቱን አውቃ ለትንሽ ጊዜ ብትጎዳ ይሻልል››አልኳት
በዚህ ጉዳይ ላይ ለ30 ደቂቃ ለበለጠ ጊዜ በከረረ ሁኔታ ስንከራከር ቆየን….ከዛ የስልክ ንግግር ድምፅ ነው ሁለታችንንም ያነቃን….
እህትህ ትርሲት ከባንኮኒው ማዶ … ፊቷ በእንባ ታጥቦ…አይኖቾ ፈጠውና አውሬ መስላ ቆማለች..ሱቁ ውስጥ ገብታ እዛ የቆመችበት ቦታ መች እንደቆመች አናውቅም..ምን ያህሉን እንደሳማችንም አናውቅም….ከሁኔታዋ እንደሚታው ግን የሚበቃትን ያህል እንደሰማችን ያስታውቃል…ሁለታችንም በርግገን ጎን ለጎን ተጣብቀን ከተቀመጥንበት ተነሳን….
‹‹ለማን እየደወለች ነው?››ሁለታችንም ግራ ተጋባን፡፡ወዲያው ስልኩ ተነሳላትና ማውራት ጀመረች፡፡
‹‹አባዬ ….ያንተ ልጅ አይደለሁም እንዴ…?እማዬና ውሽማዋ ሲያወሩ ሰማው…አባዬ እኔ ያንተ ልጅ ካልሆንኩ መኖር አልፈልግም…የሌላ ሰው ልጅ መሆን በጣም ነው የሚቀፈኝ…አይ አልጠብቅህም ..በጣም ነው የምወድህ….››አለችና ስልኩን ግድግዳው ላይ ወርውራ ከሱቁ ወጥታ ተፈተለከች፡፡ልንደረስባት ሞከርን ግን ወዲያው ተሰወረችብን፡፡
‹‹ወይኔ ልጄ….ወይኔ ልጄ…››እናትዬው ተርበተበተች....እኔም የምይዝው የምጨብጠው ግራ ገባኝ….ሱቁን ዘጋንና….
‹‹ወደየት ነው የሄደችው?››ስል እናትህን ጠየቅኳት፡፡‹‹እኔ ምናውቃለው..ወደቤት ከሄደች…ሄጄ ልያት››አለችኝ
‹‹በቃ ነይ መኪና ውስጥ ግቢ››ስላት
‹‹እንዴ ..አንድ ላይ ስንሄድ..?››
‹‹አሁን እኮ ነገሮች ተደበላልቀዋል…ምንፈራው ሳይሆን የምንጋፈጠው ነው››አልኳትና እየጎተትኩ መኪናዬ ውስጥ ይዣት ገባው፡፡በየመንገዱ እየፈለግናት…ልትሄድ ትችልበታለች ብላ እናቷ የጠረጠረችበት አንድ ሁለት ቦታ አቁመን አይተን መጨረሻ ወደቤት ሄድን…መኪናውን ራቅ አድርጌ እንዳቆም አደረገችኝና…‹‹እኔ ገብቼ ልያትና ካለች እነግርሀለው..ከሌለችም ሌላ ቦታ ሄደን እንፈልጋታለን›› ብላኝ ገባች፡፡እኔም በጭንቀት እየተንቆራጠጥኩ መጠበቅ ጀመርኩ…5 ደቂቃ ..10 ደቂቃ አለፈ..ስልኬን አውጥቼ ስደውል እናትህ ሞባይል አይነሳም…ራሴን መቆጣጠር አቃተኝና የሆነው ይሁን ብዬ ወደግቢው ገባው፡፡ሳሎኑ በራፍ እንደተከፈተ ነበር…ስገባ ልጄ ኮርኒሱ ላይ ተንጠልጥላለች..እናትህ ደግሞ የገዛ ሆዷን ላይ ቢላዋ ሽጣ ተዘርራለች፡፡ይመስለኛል እናትህ ወደቤት ስትገባ እህትህ ተሰቅላ እራሷ አጥፍታ ስታያት ወዲያው አካባቢው ላይ ያገኘችውን ቢላዋ ሆዷ ውሰጥ የሻጠችው ይመስለኛል፡፡
ከዛ ደንዝዤ የምሆነው ጠፋኝ…ምን ላድርግ ..?ልጄን ከተሰቀለችበት ለማውረድ ገመድ መቁረጫ ለመፈለግ ወደውስጥ ገብቼ መቁረጫ ይዤ ስመለስ አባትህ ከውጭ ከሳሎኑ ሲገባ አየሁት፡፡በደመነፍስ ወደ ጎሮ በራፍ ሄድኩ…ዞሬ ከግቢው ወጣሁና መኪናዬ ውስጥ ገብቼ ደም እንባ እያለቀስኩ ሁኔታዎችን መከታተል ጀምርኩ፡፡ ከዛ አንተና ወንድምህ አንድ አይነት ሰማያዊ የስፖርት ልብስ ለብሳችሁ ወደቤት ስትገቡ ተመለከትኩ፡፡ ከደቂቃዎች በኃላ ፖሊሶች ሰፈሩን ወረሩት…እናንተንም አባታችሁንም ፖሊሶች ይዘዋችሁ ሲሄድ የእናትህንና የእህትህን አስከሬን በአንብላንስ ሲወሰድ ከመንገድ ማዶ መኪናዬ ውስጥ ተቀምጬ እየተመለከትኩ ነበር፡፡ ሁለቱም እራሷቸውን እንዳጠፉ እርግጠኛ ነኝ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ዘሚካኤል እንግዳው ላይ አፍጥጦ
‹‹አይ ምንም እየገባኝ አይደለም….?››አለ
ሰውዬውም ዘሚካኤል‹‹ቁጭ በል አስረዳሀለው..››አለና ወደውስጥ ገብቶ ቀድሞ ተቀመጠ…
ፀደይ ዘሚካኤልን እየጎተተች ይዛው መጣችና አስቀመጠችው…እሷም ተቀመጠችን ስልኳን አውጥታ ሪከርድ ላይ አደረገችና ሰውዬው የሚናገረውን ለመስማት ዝግጁ ሆነች፡፡
‹‹ምን ድረስ ታውቃላችሁ?››
‹‹እኔ ምንም የማውቀው ነገር የለም››ዘሚካኤል በትግስተ የለሽነት መለሰ፡፡
ፀደይ ዝም አለች‹‹ጥሩ ከመጀመሪያው ብጀምርላችሁ ችግር የለውም..እኔ እና እናትህ የልጅነት ጓደኛሞች ማለት ፍቅረኛሞች ነበርን…በጣም ነበር የምንዋደደው…..ምንጊዜም ስለመጋባትና ዕድሜ ዘመናችንን ሙሉ አብሮ ስለመኖር ነበር የምናስበው…ከዛ ድንገት አባቴ ወደአሜሪካ መሄድ አለብህ አለኝ…ብዙ ወንድሞቹ እዛ ስላሉ ሀሳቡን ላስቀይረው አልቻልኩም….አባቴን በጣም ነበር የምፈራው..ከዛ ጥያቄውን ተቀብዬ ወደአሜሪካ ሄድኩ…ለካ እሷ በወቅቱ እህትህን ፀንሳ ነበር..፡፡››
‹‹ፀንሳ ማለት …ከማን?››
‹‹ከማን ይሆናል ከእኔ ነዋ››
‹‹እና እህቴ የአንተ ልጅ ነች…?.ምንድነው የምትቀባጥረው?››
‹‹አልቀባጠርኩም..ከፈለክ አባትህን ጠይቀው …ያውቃል…እናትህ እኔ ጥያት ስለሄድኩ በጣም ተበሳጭታብኝ ስለነበር እና በዛ ላይ አርግዛ ስለነበር…ወዲያው አባትህን አገባችው…ስታገባው..ለልጇ አባት ለማግኘት አንጂ አፍቅራው አልነበረም…እሱም ይወዳት ስለነበረ ተንከባከባት….እህትህም በሰባት ወር እንደተወለደች ነበር ያሰበው…የገዛ ልጁ ነበር የምትመስለው….ስለዚህ ትርሲትን እንደልጁ አሳደጋት..ከዛ አንተ እና ወንድምህ ተወለዳችሁ፡፡እኔም ከሀያ አመት ቆይታ በኃላ ከአሜሪካ ተመለስኩ፡፡ለእሷ የነበረኝ ፍቅር ከውስጤ ስላልበረደ ፈልጌ አገኘኋት…በጣም ተበሳጭታብኝ የነበረ ቢሆንም ታፈቅረኝ ስለነበረ በሂደት ይቅር አለቺኝ…አባትህን ፈታ እኔን እንድተገባኝ እጨቀጭቃት ጀመር…እሷም ምንም እንኳን ከእኔ ጋር ለመጋባት በጣም ፍላጎት ቢኖራትም እናንተን መበተን ስላልፈለገች በሀሳቤ ልትስማማ አልቻለችም፡፡
እኔም እሷን ትቼ ሌላ ሴት ማግባት ብሞክርም አልቻልኩም..አቃተኝ…ከዛ በቃ አንቺ እሺ ብለሽ ባልሽን ፈተሸ ማታገቢኝ ከሆነ ቢያንስ ልጄን የማግኘት መብት አለኝ..ለልጄ አባቷ እኔ እንደሆንኩ ንገሪያት እያልኩ በዚህ መጨቃጨቅ ጀመርን፡፡እሷም ያንን ማድረግ አልችልም እያለች መከላከል ጀመረች፡፡በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን በድብቅ እየተገናኘን ፍቅራችንን እንወጣ ነበር…
‹‹ለምን ያህል ጊዜ ከአባቴ እየተደበቃችሁ ..እንደዛ አደረጋችሁ?››ግሽግሽ ባለና ጥላቻ በተጫነው ስሜት ጠየቀው፡፡
‹‹አራት ወይም አምስት አመት››መለሰለት
‹‹እና አባቴ ይሄን ሁሉ ታሪክ ሲያውቅ ነዋ ..ቀልቡን ነስቶት ያንን ወንጀል የፈፀመው?››
‹‹አይ አይደለም…ስለዚህ ጉዳይ ሳስብ እስከዛሬ ድረስ ራሴን መቆጣጠር እስኪያቅተኝ አዝናለው..እመነኝ በጉዳዩ በጣም መፀፀት ብቻ ሳይሆን ብዙ ነገሬን አጥቼበታለው….፡፡ ስራዬን፤ ጤናዬን …ብዙ ብዙ ነገር…ብዙ ጊዜም ራሴን አጥፍቼ ከልጄ ትርሲት እና ከእናትህ ጎን ለመተኛት ሞክሬ ነበር..ግን በሆነ መንገድ እተርፋለው…መጨረሻ ይሄው እንደምታየኝ የአያቴ መንደር መጥቼ በዚህ አይነት ሁኔታ መኖር ጀመርኩ..ትንሽም ወደእዚህ ከመጣሁ ነው ጤነኛ የሆንኩት››
‹‹ሰውዬ እኔ ያንተን ፀፀት ለመስማተ ምንም አይነት ፍላጎት የለኝም..ስለዋናው ጉዳይ ንገረኝ››
‹‹ትዝ ይለኛል ቀኑ እሁድ ነበር….በእለቱ አባትህ ሞጆ የጓደኛው ለቅሶ ስለነበረ መሄዱን እናትህ ስትነግረኝ..መኪናዬን ከአዲስአበባ አስነስቼ አዳማ ሄድኩ ፡፡እናትህን ተቀጣጥረን ስለነበር ቡቲክ አገኘኋት …እሁድ በዛ ላይ ጥዋት ስለሆነ የገበያ ግር ግር አልነበረም.. ከዛ የተወሰነ ከቆየን በኃላ የተለመደ ጭቅጭቃችንን ጀመርን‹‹ …ለልጄ አባቷ መሆኔን ወይ ቀድመሽ ንገሪያት ወይ እነግራታለው››አልኳት፡፡
‹‹እሷ ቅጣውን በልዩ ሁኔታ ነው የምትወደው …አባትሽ ቅጣው አይደለም ብላት ልጄ በጣም ነው ምትጎዳው››አለቺኝ፡፡
‹‹ብትጎዳም ለጊዜው ነው…ከውሸት ጋር ለዘላለም ከምትኖር እውነቱን አውቃ ለትንሽ ጊዜ ብትጎዳ ይሻልል››አልኳት
በዚህ ጉዳይ ላይ ለ30 ደቂቃ ለበለጠ ጊዜ በከረረ ሁኔታ ስንከራከር ቆየን….ከዛ የስልክ ንግግር ድምፅ ነው ሁለታችንንም ያነቃን….
እህትህ ትርሲት ከባንኮኒው ማዶ … ፊቷ በእንባ ታጥቦ…አይኖቾ ፈጠውና አውሬ መስላ ቆማለች..ሱቁ ውስጥ ገብታ እዛ የቆመችበት ቦታ መች እንደቆመች አናውቅም..ምን ያህሉን እንደሳማችንም አናውቅም….ከሁኔታዋ እንደሚታው ግን የሚበቃትን ያህል እንደሰማችን ያስታውቃል…ሁለታችንም በርግገን ጎን ለጎን ተጣብቀን ከተቀመጥንበት ተነሳን….
‹‹ለማን እየደወለች ነው?››ሁለታችንም ግራ ተጋባን፡፡ወዲያው ስልኩ ተነሳላትና ማውራት ጀመረች፡፡
‹‹አባዬ ….ያንተ ልጅ አይደለሁም እንዴ…?እማዬና ውሽማዋ ሲያወሩ ሰማው…አባዬ እኔ ያንተ ልጅ ካልሆንኩ መኖር አልፈልግም…የሌላ ሰው ልጅ መሆን በጣም ነው የሚቀፈኝ…አይ አልጠብቅህም ..በጣም ነው የምወድህ….››አለችና ስልኩን ግድግዳው ላይ ወርውራ ከሱቁ ወጥታ ተፈተለከች፡፡ልንደረስባት ሞከርን ግን ወዲያው ተሰወረችብን፡፡
‹‹ወይኔ ልጄ….ወይኔ ልጄ…››እናትዬው ተርበተበተች....እኔም የምይዝው የምጨብጠው ግራ ገባኝ….ሱቁን ዘጋንና….
‹‹ወደየት ነው የሄደችው?››ስል እናትህን ጠየቅኳት፡፡‹‹እኔ ምናውቃለው..ወደቤት ከሄደች…ሄጄ ልያት››አለችኝ
‹‹በቃ ነይ መኪና ውስጥ ግቢ››ስላት
‹‹እንዴ ..አንድ ላይ ስንሄድ..?››
‹‹አሁን እኮ ነገሮች ተደበላልቀዋል…ምንፈራው ሳይሆን የምንጋፈጠው ነው››አልኳትና እየጎተትኩ መኪናዬ ውስጥ ይዣት ገባው፡፡በየመንገዱ እየፈለግናት…ልትሄድ ትችልበታለች ብላ እናቷ የጠረጠረችበት አንድ ሁለት ቦታ አቁመን አይተን መጨረሻ ወደቤት ሄድን…መኪናውን ራቅ አድርጌ እንዳቆም አደረገችኝና…‹‹እኔ ገብቼ ልያትና ካለች እነግርሀለው..ከሌለችም ሌላ ቦታ ሄደን እንፈልጋታለን›› ብላኝ ገባች፡፡እኔም በጭንቀት እየተንቆራጠጥኩ መጠበቅ ጀመርኩ…5 ደቂቃ ..10 ደቂቃ አለፈ..ስልኬን አውጥቼ ስደውል እናትህ ሞባይል አይነሳም…ራሴን መቆጣጠር አቃተኝና የሆነው ይሁን ብዬ ወደግቢው ገባው፡፡ሳሎኑ በራፍ እንደተከፈተ ነበር…ስገባ ልጄ ኮርኒሱ ላይ ተንጠልጥላለች..እናትህ ደግሞ የገዛ ሆዷን ላይ ቢላዋ ሽጣ ተዘርራለች፡፡ይመስለኛል እናትህ ወደቤት ስትገባ እህትህ ተሰቅላ እራሷ አጥፍታ ስታያት ወዲያው አካባቢው ላይ ያገኘችውን ቢላዋ ሆዷ ውሰጥ የሻጠችው ይመስለኛል፡፡
ከዛ ደንዝዤ የምሆነው ጠፋኝ…ምን ላድርግ ..?ልጄን ከተሰቀለችበት ለማውረድ ገመድ መቁረጫ ለመፈለግ ወደውስጥ ገብቼ መቁረጫ ይዤ ስመለስ አባትህ ከውጭ ከሳሎኑ ሲገባ አየሁት፡፡በደመነፍስ ወደ ጎሮ በራፍ ሄድኩ…ዞሬ ከግቢው ወጣሁና መኪናዬ ውስጥ ገብቼ ደም እንባ እያለቀስኩ ሁኔታዎችን መከታተል ጀምርኩ፡፡ ከዛ አንተና ወንድምህ አንድ አይነት ሰማያዊ የስፖርት ልብስ ለብሳችሁ ወደቤት ስትገቡ ተመለከትኩ፡፡ ከደቂቃዎች በኃላ ፖሊሶች ሰፈሩን ወረሩት…እናንተንም አባታችሁንም ፖሊሶች ይዘዋችሁ ሲሄድ የእናትህንና የእህትህን አስከሬን በአንብላንስ ሲወሰድ ከመንገድ ማዶ መኪናዬ ውስጥ ተቀምጬ እየተመለከትኩ ነበር፡፡ ሁለቱም እራሷቸውን እንዳጠፉ እርግጠኛ ነኝ፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ዘሚካኤል ስቲዲዬ ቆይቶ ገና ወደቤት እንደገባ ነበር ስልኩ የጠራው፡፡
የደወለችለት አዲስ አለም ነበረች፡፡የጠበቀው ሚካኤል ይደውልልኛል ብሎ ነበር ፡፡ከአባቱ ጋር የሚገናኙበትን ቀን ከወህኒ ቤቱ አስተዳዳሪ ጋር ተነጋግሮ እንደሚደውልለት ነገሮት ነበር፡፡እና ይሄን ቀን በፍርሀትና በጉጉት ነበር እየጠበቀ ያለው፡፡ስለአባቱ ዜና ለመስማት፡፡ስልኩን አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ አዲስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንተስ?››
‹‹እኔ በጣም ደህና ነኝ…ሚካኤል ይደውልልኛል ብዬ እየጠበቅኩ ነበር፡፡››
‹‹ይደውልልሀል..አሁን ኩማንደሩ ቀጥሮት ሊያገኘው ሄዶል …ከእሱ እንደጨረሰ እርግጠኛ ነኝ ይደውልልሀል፡፡…አታስብ ኩማንደሩ ደግሞ ያንተ አድናቂ ስለሆነ ከአባታችሁ እንድትገናኙ ሁኔታውን ያመቻቻል….በዛ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው
‹‹ጥሩ ታዲያ አንቺ ሰላም ነሽ?››
‹‹በጣም ሰላም ነኝ…ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ነበር››
‹‹ምን?››
‹‹ከፀዲ ጋር እንዴት ናችሁ?››
ያልጠበቀውን ጥያቄ ነው የጠየቀችው‹‹በጣም አሪፍ ነን…ከቦንጋ ከተመለስን በኋላ በአካል ባንገናኝም በስልክ ግን በቀን ሁለት ሶስት ጊዜ እንደዋወላለን…እንደውም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ከከተማ ወጣ ብለን ለማሳለፍ ተነጋግረናል፡፡
ግን ምነው ጠየቅሺኝ?››
‹‹ግልፅ ሆነህ ንገረኝ…ስለእሷ ምን ታስባለህ..ማለቴ አሁንም በፊት እንደነገርከኝ ታፈቅራታለህ?››
‹‹እንዴ!እንዴት በአንድ ወር ፍቅሩ ይተናል ብለሽ አሰብሽ? እንደውም ጥሩ ነገር አነሳሽልኝ…የሆነ ቀን አመቻችቼ ካንቺ ጋር መነጋገር እፈልግ ነበር..እኔ ላገባት እፍልጋለው..በቅርብ ቀን..እና እንዴት ጠይቄ ላሳምናት የሚለውን ከእኔ ይልቅ አንቺ ስለምታውቂ እንድታማክሪኝ እፈልጋለው፡፡››
‹‹እንግዲያው እንደዛ ከሆነ ሳይረፍድብህ ፍጠን››
‹‹አልገባኝም?››
‹‹ያንተን ልጅ አርግዛለች..››
የሰማውን ነገር ማመን አልቻለም…በደስታ ጮኸ…
‹‹ማለት…በፈጣሪ እየዋሸሺኝ አይደለም አይደል? ››
‹‹አርግዛለች..ለእኔም አልነገረችኝም ፡፡
በአጋጣሚ አንድ የግል ሆስፒታል ካርድ ክፍል የምትሰራ ወዳጅ ነበረችኝ …አሁን ከደቂቃዎች በፊት ደውላ ጓደኛሽ ፀንሳ እኛ ሆስፒታል ለማስወረድ መጥታ ነበር…ብላ ነገረችኝ፡፡መጀመሪያ አላመንኩም ነበር..በኋላ ግን ሆስፒታሉ ድረስ ሄጄ በሌላ መንገድ እራሷ መሆኗን አረጋግጬያለው…ልታስወርደው ለተነገወዲያ ቀጠሮ አሲይዛለች….ቀጥታ ላናግራት ፍልጌ ነበር….ጭራሽ እልክ ትጋባለች ብዬ ስለፈራሁ ምንም ልላት አልቻልኩም…አንተ ምታደርገው ነገር ካለ ሞክር››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..ለእኔ አረገዘችልኝ…..››በበቃ ቻው አዲስ አንቺ አትጨነቂ እኔ አስተካክለዋለው፡፡
የአዲስን ስልክ ከዘጋ በኃላ ቀጥታ ልብሶቹ በሻንጣ መክተት ነው የጀመረው፡፡ሁለት ሻንጣ ልብስና በወሳኝ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ሰበሰበና አፓርታማውን ለቆ ወጣ …ቀጥታ ወደአዳማ ነው የነዳው፡፡
ፀአዳ ቤት ሲደርስ በራፏ ዝግ ነበር..ሊደውልላት አልፈለገም ፡፡ሻንጣውን አወረደና በራፏ በረንዳ ላይ አድርጎ እሱ መኪናው ውስጥ ሆኖ መጠበቅ ጀመረ…ከምሽቱ አንድ ሰአት ስትመጣ እሱ መኪና ውስጥ ሻንጣው በረንዳ ላይ ሆኖ ስታየው ፍፁም ነው ግራ የተጋባችው…ምስር እሱ መሆኑን ስታውቅ ከእናቷ ተነጥላ ወደእሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ፈጥኖ ከመኪናው ወረደና እጇቹን እንደክንፍ ዘርግቶ ጠበቃት…ተጠምጥማበት በደስታ ጉንጩን ትስመው ጀመር…
ወደቤት እንደገቡ ፀደይ‹‹ምንድነው ጉዱ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምንም ..ለጥቂት ሳምንታት እረፍት ስለሆንኩ እዚህ ከእናንተ ጋር ለመቆየት ወስኜ ነው፡፡››
‹‹እዚህ ከእኛ ጋር?››
‹‹አዎ ከእናንተ ጋር››
ህፃኖ ምስር ‹‹ታድለን…ታድለን›› እያለች መጨፈር ጀመረች፡፡
ፀአዳ ልጇ ምስር ፊት ምንም ማለት አልቻለችም.‹‹እንግዲያው እደቤትህ ዘና በል…እኔ ልብስ ልቀይር ››አለችና መኝታ ቤት ገባች፡፡ከዛ እራት ሰርታ በሉና ከሶስት ሰዓት በኃላ ምስርን አስተኝተው ነበር እንደአዲስ ጭቅጭቁን የጀመሩት፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንደምታገቢኝ ቃል ገብተሸ ቀለበት እስክታስሪልኝ ድረስ ከዚህ ቤት ወጥቼ ወደቤቴ አልመለስም››ሲል ቁርጡን ፍርጥም ብሎ ነገራት፡
‹‹ጭራሽ ማግባት? እየቀለድክ ነው፡፡››
‹‹በፍፅም …ብቀልድ ነው እንደዚህ አይነት እርምጃ የወሰድኩት፡፡››
‹‹ስማ..እኔ ካንተ ጋብቻ ፍቅር ምናምን አልፈልግም››
‹‹ታዲያ ምንድንው ምትፈልጊው?››
ትኩር ብላ አየችው….
‹‹ንገሪኝ ከእኔ ምንድነው የምትፈልጊው….. ?››
‹‹ካንተ ወሲብ ብቻ ይበቃኛል….ማለቴ እስከአሁን የደረግነውን ለማለት ነው …ደግሞ አሁንም እናድረግ እያልኩህ አይደለም፡፡››
በንግግሯ ሆድን እስኪያመው ሳቀ…በመሀል ስልክ ተደወለለት ..ከወንድሙ ነበር…በጉጉት አነሳው‹‹እሺ ሚካኤል ደህና አመሸህ?››
‹‹ሰላም ነኝ…ነገ ጥዋት ሶስት ሰዓት ላይ አዳማ መገኘት ትችላለህ?››
‹‹ምነው ?አባዬን እንድናገኝ ፈቀዱልን እንዴ?››
‹‹አዎ በጣም ደስ የሚለው ደግሞ አንድ ላይ እንድናገኘው ነው ያመቻቹልን ቅር ካላለህ አዲስንና ቅዱስንም ይዘናቸው እንሄዳለን››
‹‹አረ ቅር አይለኝም ጥሩ ሀሳብ …ግን አባዬ እኔን ለማናገር ፍቃደኛ የሚሆን ይመስልሀል?››ሰሞኑን ሲብሰለሰልበት የነበረውን ስጋቱን አንስቶ ጠየቀው፡፡
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ…ከመሞቱ በፊት ማግኘት የሚፈልገው ብቸኛ ነገር እኮ አንተን ማናገር ነው…በደስታ ነው የሚያነባው….እንኳን በአካል አግኝተሀው አባዬ ብለህ ስጠራው ሰምቶ ይቅርና ባለፈው ፎቶህን ሳሳየው እንዴት እያገላበጠ ሲስምና ሲያለቅስ እንደነበረ እኔ ነኝ የማውቀው…በል በዛ እርግጠኛ ሁን..ምንም አትጨናነቅ፡፡››
‹‹ምን ያስፈልገዋል…?ማለት ምን ይዤለት ልሂድ?››
‹‹የሚያስፈልገወን ነገር ሁሉ አዘጋጅተናል…አንተ ደግሞ ሚፈልገውን ነገር እንጠይቀውና በሚቀጥለው ዙር ትወስድለታለህ…ደግሞ ደስ የሚለው ከቦንጋ ያመጣችሁትን ከዶ/ሩ ጋር ያደረጋችሁትን ውይይት ለኩማንደሩ አሰምቼው በጣም ነው ያዘነው..እናም አባዬን ከሌሎች እስረኞች ጋር ተቀላቅሎ እንዲኖር ወስነዋል…››
‹‹በጣም የሚያስደስት ነገር ነው እየነገርከኝ ያለሀው..ወንድሜ በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንክ ታውቃለህ አይደል… በጣም ነው የምኮራብህ፡፡››
ሚካኤልም እንባ እየተናነቀው‹‹እኔም በጣም ነው የምኮራብህ››አለው
‹‹በቃ እሺ …...ሶስት ሰዓት ነው ያልከኝ አይደል?፡፡››
‹‹አዎ…መድረስ ትችላለህ አይደል…?››
‹‹በደንብ እንጂ ሁለት ተኩል ደርሼ ደውልልሀለው››
‹‹ጥሩ በቃ ደህና እደር››ስልኩን ዘጋ፡፡
ንግግራቸውን ሁሉ በገረሜታ ስትሰማ የነበረችው ፀደይ‹‹እርግጠኛ ነህ ግን ሁለት ተኩል ትደርሳለህ?››ስትል በፈገግታ አሾፈችበት፡፡
‹‹ትቆጪኛለሽ ብዬ ነው እንጂ እዚህ ነኝ ልለው ነበረ››
‹‹ልፋ ቢልህ ነው ….ግን ለእናንተ ደስ ብሎኛል››
‹‹ማለት?››
‹‹አንተና ወንድምህ እንዲህ እየተደዋወላችሁ በሰላም ማውራት መቻላችሁ ትልቅ ነገር ነው…አረ እንደውም ከመነጋጋርም አልፋችሁ መሞጋገስ ጀምራችኃል››
‹‹እድሜ ለአንቺ ….ባንቺ ቀናነትና ጥረት ነው ለዚህ የበቃነው….››
‹‹እኔን ማሞገሱን እንኳን ለሌላ ጊዜ አቆየው..በነገራችን ላይ የአባትህ ጉዳይ ላይ ይግባኝ ለመጠየቅ ሚቻል ከአሆነ አንድ ጎበዝ ጠበቃ አግኝኝቼ ሁኔታውን አስረድቼው ነበር….››
‹‹በእውነት ..ታዲያ ምን አለሽ?››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
/////
ዘሚካኤል ስቲዲዬ ቆይቶ ገና ወደቤት እንደገባ ነበር ስልኩ የጠራው፡፡
የደወለችለት አዲስ አለም ነበረች፡፡የጠበቀው ሚካኤል ይደውልልኛል ብሎ ነበር ፡፡ከአባቱ ጋር የሚገናኙበትን ቀን ከወህኒ ቤቱ አስተዳዳሪ ጋር ተነጋግሮ እንደሚደውልለት ነገሮት ነበር፡፡እና ይሄን ቀን በፍርሀትና በጉጉት ነበር እየጠበቀ ያለው፡፡ስለአባቱ ዜና ለመስማት፡፡ስልኩን አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ አዲስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንተስ?››
‹‹እኔ በጣም ደህና ነኝ…ሚካኤል ይደውልልኛል ብዬ እየጠበቅኩ ነበር፡፡››
‹‹ይደውልልሀል..አሁን ኩማንደሩ ቀጥሮት ሊያገኘው ሄዶል …ከእሱ እንደጨረሰ እርግጠኛ ነኝ ይደውልልሀል፡፡…አታስብ ኩማንደሩ ደግሞ ያንተ አድናቂ ስለሆነ ከአባታችሁ እንድትገናኙ ሁኔታውን ያመቻቻል….በዛ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው
‹‹ጥሩ ታዲያ አንቺ ሰላም ነሽ?››
‹‹በጣም ሰላም ነኝ…ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ነበር››
‹‹ምን?››
‹‹ከፀዲ ጋር እንዴት ናችሁ?››
ያልጠበቀውን ጥያቄ ነው የጠየቀችው‹‹በጣም አሪፍ ነን…ከቦንጋ ከተመለስን በኋላ በአካል ባንገናኝም በስልክ ግን በቀን ሁለት ሶስት ጊዜ እንደዋወላለን…እንደውም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ከከተማ ወጣ ብለን ለማሳለፍ ተነጋግረናል፡፡
ግን ምነው ጠየቅሺኝ?››
‹‹ግልፅ ሆነህ ንገረኝ…ስለእሷ ምን ታስባለህ..ማለቴ አሁንም በፊት እንደነገርከኝ ታፈቅራታለህ?››
‹‹እንዴ!እንዴት በአንድ ወር ፍቅሩ ይተናል ብለሽ አሰብሽ? እንደውም ጥሩ ነገር አነሳሽልኝ…የሆነ ቀን አመቻችቼ ካንቺ ጋር መነጋገር እፈልግ ነበር..እኔ ላገባት እፍልጋለው..በቅርብ ቀን..እና እንዴት ጠይቄ ላሳምናት የሚለውን ከእኔ ይልቅ አንቺ ስለምታውቂ እንድታማክሪኝ እፈልጋለው፡፡››
‹‹እንግዲያው እንደዛ ከሆነ ሳይረፍድብህ ፍጠን››
‹‹አልገባኝም?››
‹‹ያንተን ልጅ አርግዛለች..››
የሰማውን ነገር ማመን አልቻለም…በደስታ ጮኸ…
‹‹ማለት…በፈጣሪ እየዋሸሺኝ አይደለም አይደል? ››
‹‹አርግዛለች..ለእኔም አልነገረችኝም ፡፡
በአጋጣሚ አንድ የግል ሆስፒታል ካርድ ክፍል የምትሰራ ወዳጅ ነበረችኝ …አሁን ከደቂቃዎች በፊት ደውላ ጓደኛሽ ፀንሳ እኛ ሆስፒታል ለማስወረድ መጥታ ነበር…ብላ ነገረችኝ፡፡መጀመሪያ አላመንኩም ነበር..በኋላ ግን ሆስፒታሉ ድረስ ሄጄ በሌላ መንገድ እራሷ መሆኗን አረጋግጬያለው…ልታስወርደው ለተነገወዲያ ቀጠሮ አሲይዛለች….ቀጥታ ላናግራት ፍልጌ ነበር….ጭራሽ እልክ ትጋባለች ብዬ ስለፈራሁ ምንም ልላት አልቻልኩም…አንተ ምታደርገው ነገር ካለ ሞክር››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..ለእኔ አረገዘችልኝ…..››በበቃ ቻው አዲስ አንቺ አትጨነቂ እኔ አስተካክለዋለው፡፡
የአዲስን ስልክ ከዘጋ በኃላ ቀጥታ ልብሶቹ በሻንጣ መክተት ነው የጀመረው፡፡ሁለት ሻንጣ ልብስና በወሳኝ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ሰበሰበና አፓርታማውን ለቆ ወጣ …ቀጥታ ወደአዳማ ነው የነዳው፡፡
ፀአዳ ቤት ሲደርስ በራፏ ዝግ ነበር..ሊደውልላት አልፈለገም ፡፡ሻንጣውን አወረደና በራፏ በረንዳ ላይ አድርጎ እሱ መኪናው ውስጥ ሆኖ መጠበቅ ጀመረ…ከምሽቱ አንድ ሰአት ስትመጣ እሱ መኪና ውስጥ ሻንጣው በረንዳ ላይ ሆኖ ስታየው ፍፁም ነው ግራ የተጋባችው…ምስር እሱ መሆኑን ስታውቅ ከእናቷ ተነጥላ ወደእሱ መሮጥ ስትጀምር እሱም ፈጥኖ ከመኪናው ወረደና እጇቹን እንደክንፍ ዘርግቶ ጠበቃት…ተጠምጥማበት በደስታ ጉንጩን ትስመው ጀመር…
ወደቤት እንደገቡ ፀደይ‹‹ምንድነው ጉዱ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹ምንም ..ለጥቂት ሳምንታት እረፍት ስለሆንኩ እዚህ ከእናንተ ጋር ለመቆየት ወስኜ ነው፡፡››
‹‹እዚህ ከእኛ ጋር?››
‹‹አዎ ከእናንተ ጋር››
ህፃኖ ምስር ‹‹ታድለን…ታድለን›› እያለች መጨፈር ጀመረች፡፡
ፀአዳ ልጇ ምስር ፊት ምንም ማለት አልቻለችም.‹‹እንግዲያው እደቤትህ ዘና በል…እኔ ልብስ ልቀይር ››አለችና መኝታ ቤት ገባች፡፡ከዛ እራት ሰርታ በሉና ከሶስት ሰዓት በኃላ ምስርን አስተኝተው ነበር እንደአዲስ ጭቅጭቁን የጀመሩት፡፡
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹እንደምታገቢኝ ቃል ገብተሸ ቀለበት እስክታስሪልኝ ድረስ ከዚህ ቤት ወጥቼ ወደቤቴ አልመለስም››ሲል ቁርጡን ፍርጥም ብሎ ነገራት፡
‹‹ጭራሽ ማግባት? እየቀለድክ ነው፡፡››
‹‹በፍፅም …ብቀልድ ነው እንደዚህ አይነት እርምጃ የወሰድኩት፡፡››
‹‹ስማ..እኔ ካንተ ጋብቻ ፍቅር ምናምን አልፈልግም››
‹‹ታዲያ ምንድንው ምትፈልጊው?››
ትኩር ብላ አየችው….
‹‹ንገሪኝ ከእኔ ምንድነው የምትፈልጊው….. ?››
‹‹ካንተ ወሲብ ብቻ ይበቃኛል….ማለቴ እስከአሁን የደረግነውን ለማለት ነው …ደግሞ አሁንም እናድረግ እያልኩህ አይደለም፡፡››
በንግግሯ ሆድን እስኪያመው ሳቀ…በመሀል ስልክ ተደወለለት ..ከወንድሙ ነበር…በጉጉት አነሳው‹‹እሺ ሚካኤል ደህና አመሸህ?››
‹‹ሰላም ነኝ…ነገ ጥዋት ሶስት ሰዓት ላይ አዳማ መገኘት ትችላለህ?››
‹‹ምነው ?አባዬን እንድናገኝ ፈቀዱልን እንዴ?››
‹‹አዎ በጣም ደስ የሚለው ደግሞ አንድ ላይ እንድናገኘው ነው ያመቻቹልን ቅር ካላለህ አዲስንና ቅዱስንም ይዘናቸው እንሄዳለን››
‹‹አረ ቅር አይለኝም ጥሩ ሀሳብ …ግን አባዬ እኔን ለማናገር ፍቃደኛ የሚሆን ይመስልሀል?››ሰሞኑን ሲብሰለሰልበት የነበረውን ስጋቱን አንስቶ ጠየቀው፡፡
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ…ከመሞቱ በፊት ማግኘት የሚፈልገው ብቸኛ ነገር እኮ አንተን ማናገር ነው…በደስታ ነው የሚያነባው….እንኳን በአካል አግኝተሀው አባዬ ብለህ ስጠራው ሰምቶ ይቅርና ባለፈው ፎቶህን ሳሳየው እንዴት እያገላበጠ ሲስምና ሲያለቅስ እንደነበረ እኔ ነኝ የማውቀው…በል በዛ እርግጠኛ ሁን..ምንም አትጨናነቅ፡፡››
‹‹ምን ያስፈልገዋል…?ማለት ምን ይዤለት ልሂድ?››
‹‹የሚያስፈልገወን ነገር ሁሉ አዘጋጅተናል…አንተ ደግሞ ሚፈልገውን ነገር እንጠይቀውና በሚቀጥለው ዙር ትወስድለታለህ…ደግሞ ደስ የሚለው ከቦንጋ ያመጣችሁትን ከዶ/ሩ ጋር ያደረጋችሁትን ውይይት ለኩማንደሩ አሰምቼው በጣም ነው ያዘነው..እናም አባዬን ከሌሎች እስረኞች ጋር ተቀላቅሎ እንዲኖር ወስነዋል…››
‹‹በጣም የሚያስደስት ነገር ነው እየነገርከኝ ያለሀው..ወንድሜ በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንክ ታውቃለህ አይደል… በጣም ነው የምኮራብህ፡፡››
ሚካኤልም እንባ እየተናነቀው‹‹እኔም በጣም ነው የምኮራብህ››አለው
‹‹በቃ እሺ …...ሶስት ሰዓት ነው ያልከኝ አይደል?፡፡››
‹‹አዎ…መድረስ ትችላለህ አይደል…?››
‹‹በደንብ እንጂ ሁለት ተኩል ደርሼ ደውልልሀለው››
‹‹ጥሩ በቃ ደህና እደር››ስልኩን ዘጋ፡፡
ንግግራቸውን ሁሉ በገረሜታ ስትሰማ የነበረችው ፀደይ‹‹እርግጠኛ ነህ ግን ሁለት ተኩል ትደርሳለህ?››ስትል በፈገግታ አሾፈችበት፡፡
‹‹ትቆጪኛለሽ ብዬ ነው እንጂ እዚህ ነኝ ልለው ነበረ››
‹‹ልፋ ቢልህ ነው ….ግን ለእናንተ ደስ ብሎኛል››
‹‹ማለት?››
‹‹አንተና ወንድምህ እንዲህ እየተደዋወላችሁ በሰላም ማውራት መቻላችሁ ትልቅ ነገር ነው…አረ እንደውም ከመነጋጋርም አልፋችሁ መሞጋገስ ጀምራችኃል››
‹‹እድሜ ለአንቺ ….ባንቺ ቀናነትና ጥረት ነው ለዚህ የበቃነው….››
‹‹እኔን ማሞገሱን እንኳን ለሌላ ጊዜ አቆየው..በነገራችን ላይ የአባትህ ጉዳይ ላይ ይግባኝ ለመጠየቅ ሚቻል ከአሆነ አንድ ጎበዝ ጠበቃ አግኝኝቼ ሁኔታውን አስረድቼው ነበር….››
‹‹በእውነት ..ታዲያ ምን አለሽ?››