#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አማላጅ
ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡
መጣራታቸውን ትተው "ደህና አደራችሁ መልካሙ" ? አሉ፡፡ ቄስ አሻግሬ ፤
አቀርቅረው ከሚያነቡት መፅሃፍ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው "እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደሩ" ? አሉ ፡፡ ቄስ መልካሙ፡፡ ንስሃ አባታቸው ያለወትሯቸው በጥዋት በመምጣታቸው የመደናገጥ ምልክት እየታየባቸው ፡፡ ፀበል ሊረጩን ይሆን ? ሳንነግራቸውና ሳንዘጋጅ ፤ እነሱም ሳይነግሩን ፤ በሰላም ይሆን የመጡት? ከራሳቸው ሃሳብ ሳይወጡ የተናገሩት ነበር
"አንተን ፈልጌ ነበር የመጣሁት"፡፡ እደጅ ላግኝህ አሉ ቄስ አሻግሬ ፡፡ ለስለስ ባለ አነጋገር ፡፡
"ለምን እንደተፈለጉ ባያውቁም "ምነው ደህና አይደሉም እንዴ"?
አይ ደህና ነኝ ፡፡ ለጉዳይ ፈልጌህ ነበር አሉ
ከየት መጀመር እንዳለባቸው ግራ ቢገባቸውም "አቶ ለማ ልጅህን ለልጄ እንዲሰጡኝ አማላጅ ሂድልኝ ብሎኝ ነው የመጣሁት"፡፡ ብለው ሃሳባቸውን ሳያቋርጡ በመቀጠል አቶ ለማ ሽፈራው ጥሩ ሰው ናቸው፡፡ ዘራቸውም ቢሆንም ምንም አይወጣለትም ፡፡ ልጁም የተባረከ ፤ የተመሰገነ ፤ ጨዋ ፤ ድምፁም የማይሰማ ማለፊያ ገበሬ ነው" አሉ፡፡
ቄስ መልካሙ ያልጠበቁትና ያላሰቡት ነገር ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው ምን ማለት እንዳለባቸው አብሰለሰሉ፡፡ የማይሆን ነገር ነው፡፡ አሁን እድላዊትን አግቢ ብላት ትምህርቷን ትታ የምታገባ አይመስለኝም፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር እየተሟገቱ ከቆዩ በኋላ "እንግዲህ
ከቤተሰብና ዘመድ ጋር መክረን መልስ ብንሰጥ ይሻላል፡፡ አሁን እኔ ለብቻየ የምወስነው ነገር የለም" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመባባት እያለም ቢሆን፡፡
"ታዲያ ቀነ ቀጠሮው ለመቼ ይሁን" ? አሉ፡፡ መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል የአገሩ ባህልና የተለመደ መሆኑን ስለሚያውቁ ፡ተመልሰው የሚመጡበትን ቀን በጉጉት ለመስማት እየጠበቁ ፡፡
"ዛሬ ቀኑ ሮዕብ አይደለም፡፡ የዛሬ አስራ አምስት ቀን ይመለሱ፡፡ እኛም እስከዛ ብንመካከርበት ይሻላል" በማለት መልስ ሰጧቸው፡፡
ይሁን መልካም ነው፡፡ ብለው የተሰጣቸውን ቀነ ቀጠሮ ተቀብለው ከቄስ መልካሙ ጋር ተሰነባብተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ንሰሃ አባታቸውን ከሸኙ በኋላ ፤ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ በመጨጊያቸው ላይ ተቀመጡ፡፡ አገጫቸውን በቀኝ እጃቸው ደገፍ አደረጉ፡፡ ትክዝ ባለ አንደበት ስለልጃቸው እድላዊት በውስጣቸው ማብሰልሰል ተያያዙት፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ከማድቤት ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤት እየሄዱ ባለቤታቸው ከወትሯቸው በተለየ ተክዘው ተመለከቷቸው፡፡ እርምጃቸውን ገታ አድርገው "ምነው ቄስ አሻግሬ አመጣጣቸው በደህና አይደለም እንዴ"? አሉ ፤ ለባለቤታቸው ፡፡
"አይ ደህና" ናቸው ፤ አሉ፡፡ ሃዘን ይሁን ትካዜ በተቀላቀለበት ንግግር፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የንሰሃ አባታቸው ዛሬ በጥዋት አመጣጣቸው ለምን እንደሆነ ባያውቁም የባለቤታቸው መተከዝ አስጨንቋቸዋል፡፡ "በሰላምማ አልመሰለኝም" አሉ፡፡ ወደ ባለቤታቸው እየተጠጉ፡፡
"የመጡትስ በሰላም ቢሆንም አቶ ለማ ሽፈራው አማላጅ ልከዋቸው ነው የመጡት" አሉ፡፡ የባለቤታቸውን ሁኔታ እየተመለከቱ፡፡
"የምን አማላጅ ነው?" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመርበትበት እያለ፡፡ የምን አማላጅነት እንደሆነ ለመስማት በመቸኮል፡፡
የአቶ ለማን ልጅ ታውቂዋለሽ ?"፡፡
"ትንሹን ነው ትልቁን?፡፡
"አይ! ትንሹን ይሁን ትልቁን አለየሁትም፡፡ አበበ የሚባለውን፡፡
ምን እንደሆነ ሳያውቁ "በሞትኩት ምን ነካው ያምስኪን ልጅ ከሰው ተጣላ" እንዴ ?፡፡
"እሱስ አልተጣላም፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው እድላዊትን ለአበበ ስጡኝ ብሎ ነው፡፡ ቄስ አሻግሬን አማላጅ ተልከው የመጡት"፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ለመስማት የጓጉትና ልባቸው ተንጠልጥሎ ሲጠብቁት የነበረው ምን እንደ ሆነ ባያውቁም ከባለቤታቸው የሰሙት ያልጠበቁትና ያላሰቡት ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው መርዶ እንደ ተነገራቸው ያህል በዝምታ ተዋጡ፡፡ በሃሳባቸው ልጄን እማ አልሰጥም አስተምራለሁ፡፡ ትምህርቷን ሳትጨርስ አልድራትም፡፡ እሷም እሽ አትልም በዛ ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተባለች አገር የመሰከረላት ነች ፡፡ የልጃቸውን ሃሳብ እያወጡና እያወረዱ ከሔዱበት የሃሳብ ሰመመን ሳይመለሱ..
እና "አሁን ምን ይሻላል ትያለሽ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡ ከነጎዱበት የሃሳብ ሰመመን መለስ ብለው "እኔ ምን እላለሁ አንተ ምን አልካቸው?፡፡
"እኔማ ለዛሬ አስራምስት ቀን ተመልሰው እንዲመጡ ቀጥሪያቸዋለሁ፡፡ እኛም መመካከርና የእድላዊትን ፈቃድ ማወቅ ስላለብን ብየ ነው፡፡ ቀኑን ያስረዘምኩት፡፡ ለመሆኑ የሚሳካ ይመስልሻል ?፡፡
"እኔ እድላዊት ለማግባት እሽ የምትል አይመስለኝም፡፡በዛ ላይ ለትምህርቷ ያላት ፍላጎት ጎበዝ ተማሪ እንደሆነች ማንም ያውቃታል፡፡ እንደ እኔ ሃሳብ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ፤ ብታገባ ይሻላል፡፡ ትዳር ይደረሳል፡፡ የት እንዳትሔድ ነው፡፡ ብለው አሁን አንተ ምን ወሰንክ አሉ?፡፡
"ማድረግ ያለብንማ ሁለታችንም ተመካክረን መወሰን ነው፡፡ እንደ እኔ እድላዊት እሷ እንኳን ባትፈቅድም ማግባት አለባት፡፡ ለትዳር ደርሳለች፡፡ ትምህርቷም ይበቃታል፡፡ ከአሁን በኋላ፤ ከትምህርቷ ቀርታ የቤት ሙያ መልመድ አለባት" አሉ፡፡
እድላዊት እንደ እናቷ የጠይም ቆንጆ ሰለክለክ ያለች ፤ ቁመናዋ እና ጥርሶቿ ልክ እንደ አባቷ ከሩቅ የሚያማልል ነው፡፡ ታዲያ የጠይም መልከመልካሟን ቆንጆ እንድላዊትን የሚያያት ሁሉ ሳይጎመዣት
አያልፍም ነበር ፡፡
አበበ ለማ እድላዊትን ሊያገባት አማላጅ የላከው በአጋጣሚ ከወንድሟ ከተመስገን ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ባያት ማግስት ነበር፡፡ለቤተሰቦቹ ነግሮ አማላጅ እንዲላክለት ያደረገው፡፡
ወ/ሮ አሰገደች እድላዊትን አልድርም ፤ አስተምራለሁ ፤ እያሉ በሃሳባቸውም ሲፎክሩ የነበሩት በባለቤታቸው ቁጣ ያዘለ ንግግር ተቀየሩ፡፡
አንተ ከወሰንህ ታዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እኔም ማግባት አለባት ባይ ነኝ፡፡ ማግባቷ ለእኔም ትጠቅመኛለች፡፡ ብታመም እንኳን ጠያቂ ዘመድ በቅርብ የለኝ፡፡ የምታገባበት ቦታ ቅርብም በመሆኑ እየመጣች ትጠይቀኛለች፡፡ በፍራትም ቢሆን ከባለቤታቸው ሃሳብ ላለመውጣት የተናገሩት ነበር፡፡
ቄስ መልካሙ የባለቤታቸውን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ አንድ ላይ ካሰባሰቡ በኋላ፤ እድላዊትን አሁን የተባባልነውን ሁሉ ከትምህርቷ ስትመጣ ንገሪያትና ከትምህርት ቀርታ የቤት ውስጥ ስራ እንድትለምድ አድርጊያት አሉ፡፡ ቁርጥና ኮስተር ባለ ንግግር፡፡
"እሽ ነግሬያት እንድትቀር አደርጋለሁ ፡፡
እድላዊትና ተመስገን
የጥዋት ተማሪ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እድላዊት ከወትሮው በተለየ ምክንያቱ በምን እንደሆነ አላወቀችውም፡፡ ግራ ተጋብታለች ፤ ሰውነቷ ይርበተበታል፡፡ ወደ ፊት መሔዷን ተወት አድርጋ አንዳንዴ ቆም በማለት ራሷን ለማረጋጋት ትሞክራለች፡፡
ተመስገንም በእህቱ መለዋወጥና ዝምታ ግራ ገብቶታል፡፡ ከአሁን አሁን ትነግረኛለች ብሎ ቢያስብም እድላዊት ግን የሆነችውን ለራሷ አላወቀችም፡፡ ምን እንደሆነችም ልትነግረው አልቻለችም ነበር፡፡
"ምን ሆነሽ ነው አሞሻል እንዴ?፡፡
"አላመመኝም ውስጤን ግን ፍራት ፍራት ይለኛል፡፡
"ምነው በሰላም ?፡፡
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አማላጅ
ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ሙግት ገጥመዋል ፡፡ እሽ ይሉኝ ይሆን ? ወይስ እንቢ ? እንደገና ደግሞ በአንዴማ እንቢም ፤ እሽም አይሉኝም ፡፡ እያሉ ሳይታወቃቸው ቄስ መልካሙ ቤት ደረሱ፡፡ ለመጣራት ወደ አጥሩ ተጠጉ ፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ ቄስ መልካሙን ግቢያቸው ውስጥ መፅኃፍ እያነበቡ ተመለከቷቸው ፡፡
መጣራታቸውን ትተው "ደህና አደራችሁ መልካሙ" ? አሉ፡፡ ቄስ አሻግሬ ፤
አቀርቅረው ከሚያነቡት መፅሃፍ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው "እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም አደሩ" ? አሉ ፡፡ ቄስ መልካሙ፡፡ ንስሃ አባታቸው ያለወትሯቸው በጥዋት በመምጣታቸው የመደናገጥ ምልክት እየታየባቸው ፡፡ ፀበል ሊረጩን ይሆን ? ሳንነግራቸውና ሳንዘጋጅ ፤ እነሱም ሳይነግሩን ፤ በሰላም ይሆን የመጡት? ከራሳቸው ሃሳብ ሳይወጡ የተናገሩት ነበር
"አንተን ፈልጌ ነበር የመጣሁት"፡፡ እደጅ ላግኝህ አሉ ቄስ አሻግሬ ፡፡ ለስለስ ባለ አነጋገር ፡፡
"ለምን እንደተፈለጉ ባያውቁም "ምነው ደህና አይደሉም እንዴ"?
አይ ደህና ነኝ ፡፡ ለጉዳይ ፈልጌህ ነበር አሉ
ከየት መጀመር እንዳለባቸው ግራ ቢገባቸውም "አቶ ለማ ልጅህን ለልጄ እንዲሰጡኝ አማላጅ ሂድልኝ ብሎኝ ነው የመጣሁት"፡፡ ብለው ሃሳባቸውን ሳያቋርጡ በመቀጠል አቶ ለማ ሽፈራው ጥሩ ሰው ናቸው፡፡ ዘራቸውም ቢሆንም ምንም አይወጣለትም ፡፡ ልጁም የተባረከ ፤ የተመሰገነ ፤ ጨዋ ፤ ድምፁም የማይሰማ ማለፊያ ገበሬ ነው" አሉ፡፡
ቄስ መልካሙ ያልጠበቁትና ያላሰቡት ነገር ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው ምን ማለት እንዳለባቸው አብሰለሰሉ፡፡ የማይሆን ነገር ነው፡፡ አሁን እድላዊትን አግቢ ብላት ትምህርቷን ትታ የምታገባ አይመስለኝም፡፡ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር እየተሟገቱ ከቆዩ በኋላ "እንግዲህ
ከቤተሰብና ዘመድ ጋር መክረን መልስ ብንሰጥ ይሻላል፡፡ አሁን እኔ ለብቻየ የምወስነው ነገር የለም" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመባባት እያለም ቢሆን፡፡
"ታዲያ ቀነ ቀጠሮው ለመቼ ይሁን" ? አሉ፡፡ መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል የአገሩ ባህልና የተለመደ መሆኑን ስለሚያውቁ ፡ተመልሰው የሚመጡበትን ቀን በጉጉት ለመስማት እየጠበቁ ፡፡
"ዛሬ ቀኑ ሮዕብ አይደለም፡፡ የዛሬ አስራ አምስት ቀን ይመለሱ፡፡ እኛም እስከዛ ብንመካከርበት ይሻላል" በማለት መልስ ሰጧቸው፡፡
ይሁን መልካም ነው፡፡ ብለው የተሰጣቸውን ቀነ ቀጠሮ ተቀብለው ከቄስ መልካሙ ጋር ተሰነባብተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ንሰሃ አባታቸውን ከሸኙ በኋላ ፤ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ በመጨጊያቸው ላይ ተቀመጡ፡፡ አገጫቸውን በቀኝ እጃቸው ደገፍ አደረጉ፡፡ ትክዝ ባለ አንደበት ስለልጃቸው እድላዊት በውስጣቸው ማብሰልሰል ተያያዙት፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ከማድቤት ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤት እየሄዱ ባለቤታቸው ከወትሯቸው በተለየ ተክዘው ተመለከቷቸው፡፡ እርምጃቸውን ገታ አድርገው "ምነው ቄስ አሻግሬ አመጣጣቸው በደህና አይደለም እንዴ"? አሉ ፤ ለባለቤታቸው ፡፡
"አይ ደህና" ናቸው ፤ አሉ፡፡ ሃዘን ይሁን ትካዜ በተቀላቀለበት ንግግር፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የንሰሃ አባታቸው ዛሬ በጥዋት አመጣጣቸው ለምን እንደሆነ ባያውቁም የባለቤታቸው መተከዝ አስጨንቋቸዋል፡፡ "በሰላምማ አልመሰለኝም" አሉ፡፡ ወደ ባለቤታቸው እየተጠጉ፡፡
"የመጡትስ በሰላም ቢሆንም አቶ ለማ ሽፈራው አማላጅ ልከዋቸው ነው የመጡት" አሉ፡፡ የባለቤታቸውን ሁኔታ እየተመለከቱ፡፡
"የምን አማላጅ ነው?" አሉ፡፡ ሆዳቸው እንደመርበትበት እያለ፡፡ የምን አማላጅነት እንደሆነ ለመስማት በመቸኮል፡፡
የአቶ ለማን ልጅ ታውቂዋለሽ ?"፡፡
"ትንሹን ነው ትልቁን?፡፡
"አይ! ትንሹን ይሁን ትልቁን አለየሁትም፡፡ አበበ የሚባለውን፡፡
ምን እንደሆነ ሳያውቁ "በሞትኩት ምን ነካው ያምስኪን ልጅ ከሰው ተጣላ" እንዴ ?፡፡
"እሱስ አልተጣላም፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው እድላዊትን ለአበበ ስጡኝ ብሎ ነው፡፡ ቄስ አሻግሬን አማላጅ ተልከው የመጡት"፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ለመስማት የጓጉትና ልባቸው ተንጠልጥሎ ሲጠብቁት የነበረው ምን እንደ ሆነ ባያውቁም ከባለቤታቸው የሰሙት ያልጠበቁትና ያላሰቡት ሆነባቸው፡፡ ለጊዜው መርዶ እንደ ተነገራቸው ያህል በዝምታ ተዋጡ፡፡ በሃሳባቸው ልጄን እማ አልሰጥም አስተምራለሁ፡፡ ትምህርቷን ሳትጨርስ አልድራትም፡፡ እሷም እሽ አትልም በዛ ላይ ጎበዝ ተማሪ እየተባለች አገር የመሰከረላት ነች ፡፡ የልጃቸውን ሃሳብ እያወጡና እያወረዱ ከሔዱበት የሃሳብ ሰመመን ሳይመለሱ..
እና "አሁን ምን ይሻላል ትያለሽ? አሉ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡ ከነጎዱበት የሃሳብ ሰመመን መለስ ብለው "እኔ ምን እላለሁ አንተ ምን አልካቸው?፡፡
"እኔማ ለዛሬ አስራምስት ቀን ተመልሰው እንዲመጡ ቀጥሪያቸዋለሁ፡፡ እኛም መመካከርና የእድላዊትን ፈቃድ ማወቅ ስላለብን ብየ ነው፡፡ ቀኑን ያስረዘምኩት፡፡ ለመሆኑ የሚሳካ ይመስልሻል ?፡፡
"እኔ እድላዊት ለማግባት እሽ የምትል አይመስለኝም፡፡በዛ ላይ ለትምህርቷ ያላት ፍላጎት ጎበዝ ተማሪ እንደሆነች ማንም ያውቃታል፡፡ እንደ እኔ ሃሳብ ትምህርቷን ከጨረሰች በኋላ፤ ብታገባ ይሻላል፡፡ ትዳር ይደረሳል፡፡ የት እንዳትሔድ ነው፡፡ ብለው አሁን አንተ ምን ወሰንክ አሉ?፡፡
"ማድረግ ያለብንማ ሁለታችንም ተመካክረን መወሰን ነው፡፡ እንደ እኔ እድላዊት እሷ እንኳን ባትፈቅድም ማግባት አለባት፡፡ ለትዳር ደርሳለች፡፡ ትምህርቷም ይበቃታል፡፡ ከአሁን በኋላ፤ ከትምህርቷ ቀርታ የቤት ሙያ መልመድ አለባት" አሉ፡፡
እድላዊት እንደ እናቷ የጠይም ቆንጆ ሰለክለክ ያለች ፤ ቁመናዋ እና ጥርሶቿ ልክ እንደ አባቷ ከሩቅ የሚያማልል ነው፡፡ ታዲያ የጠይም መልከመልካሟን ቆንጆ እንድላዊትን የሚያያት ሁሉ ሳይጎመዣት
አያልፍም ነበር ፡፡
አበበ ለማ እድላዊትን ሊያገባት አማላጅ የላከው በአጋጣሚ ከወንድሟ ከተመስገን ጋር ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ባያት ማግስት ነበር፡፡ለቤተሰቦቹ ነግሮ አማላጅ እንዲላክለት ያደረገው፡፡
ወ/ሮ አሰገደች እድላዊትን አልድርም ፤ አስተምራለሁ ፤ እያሉ በሃሳባቸውም ሲፎክሩ የነበሩት በባለቤታቸው ቁጣ ያዘለ ንግግር ተቀየሩ፡፡
አንተ ከወሰንህ ታዲያ ምን አደርጋለሁ፡፡ እኔም ማግባት አለባት ባይ ነኝ፡፡ ማግባቷ ለእኔም ትጠቅመኛለች፡፡ ብታመም እንኳን ጠያቂ ዘመድ በቅርብ የለኝ፡፡ የምታገባበት ቦታ ቅርብም በመሆኑ እየመጣች ትጠይቀኛለች፡፡ በፍራትም ቢሆን ከባለቤታቸው ሃሳብ ላለመውጣት የተናገሩት ነበር፡፡
ቄስ መልካሙ የባለቤታቸውን ሃሳብና የራሳቸውን ሃሳብ አንድ ላይ ካሰባሰቡ በኋላ፤ እድላዊትን አሁን የተባባልነውን ሁሉ ከትምህርቷ ስትመጣ ንገሪያትና ከትምህርት ቀርታ የቤት ውስጥ ስራ እንድትለምድ አድርጊያት አሉ፡፡ ቁርጥና ኮስተር ባለ ንግግር፡፡
"እሽ ነግሬያት እንድትቀር አደርጋለሁ ፡፡
እድላዊትና ተመስገን
የጥዋት ተማሪ ናቸው፡፡ ወደ ትምህርት ቤት እየሔዱ እድላዊት ከወትሮው በተለየ ምክንያቱ በምን እንደሆነ አላወቀችውም፡፡ ግራ ተጋብታለች ፤ ሰውነቷ ይርበተበታል፡፡ ወደ ፊት መሔዷን ተወት አድርጋ አንዳንዴ ቆም በማለት ራሷን ለማረጋጋት ትሞክራለች፡፡
ተመስገንም በእህቱ መለዋወጥና ዝምታ ግራ ገብቶታል፡፡ ከአሁን አሁን ትነግረኛለች ብሎ ቢያስብም እድላዊት ግን የሆነችውን ለራሷ አላወቀችም፡፡ ምን እንደሆነችም ልትነግረው አልቻለችም ነበር፡፡
"ምን ሆነሽ ነው አሞሻል እንዴ?፡፡
"አላመመኝም ውስጤን ግን ፍራት ፍራት ይለኛል፡፡
"ምነው በሰላም ?፡፡
👍89❤11🥰1😱1🎉1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቄስ አሻግሬ
ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡
ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡
አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡
"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡
"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡
"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::
"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡
አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡
"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡
ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡
አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡
እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?
ተመስገን
ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡
እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡
ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡
የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡
ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡
ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡
ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡
የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ
"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡
እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡
ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቄስ አሻግሬ
ሔደውልኝ ይሆን? ዛሬ ደግሞ ማርያም ናት፡፡ ቅዳሴ ይኖርባቸው ይሆን? ለነገሩ ቅዳሴ እንኳን ከሰዓት ነው፡፡ ቀኑ ዕሮብ አይደለም ምናልባት ጠዋት ሄደውልኝ ይሆናል፡፡ ለማንኛውም እኔም ማህበር ስላለኝ እዛው ቤተ ክርስቲያን አገኛቸዋለሁ፡፡ ከማህበር ስንወጣ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ብሎ ከሰው ጋር ባይይሆንም ከራሱ ሃሳብ ጋር የተናገረው ነበር፡፡ አቶ ለማ ሽፈራው፡፡
ከቅዳሴ የመውጫ ሰዓት ስለደረሰ ጋቢውን ለባብሶ ተነሳ፡፡ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ቄስ አሻግሬ አማላጅነቱ ሙሉ በሙሉ ተሳክቷል ባይባልም በተወሰነ መልኩ ተስፋ የሚሰጥ መልስ በማግኘታቸው ተደስተዋል፡፡ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ከሰዓት ቅዳሴ ስለነበረባቸው ብዙም ሳይቆዩ ተነስተው ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዞዋቸውን አቀኑ፡፡
አቶ ለማ ከቅዳሴ ሲወጡ ደረሰ፡፡ ቄስ አሻግሬን ለማናገር ከማህበር በኋላ ሊመሽ ስለሚችል ዛቲ እንደቀመሱ ማናገር እንዳለበት አሰበ፡፡ ከዛቲ እንደተበተኑ ካህናት ከቅዳሴ ወጥተው ወደ ተቀመጡበት ቦታ ሔደ፡፡
"ሰላም ዋሉ ቄስ አሻግሬ” ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ሰላም ዋልህ?፡፡ ለማ" ብለው አጠፌታ መልስ ሰጥተውት መስቀል አሳለሙት፡፡ "ዛሬ ማርያም መጥተህ ኖሯል፡፡ መሃበር አለህ ለካስ" አሉ፡፡
"አዎ፤ ማህበር አለኝ"፡፡ ብሎ በቀጥታ ለማናገር ወደ ፈለገው ጉዳይ ገባ፡፡ "እንዴው እዛ ጉዳይ ጋር ሔደውልኝ ነበር ?"፡፡
"አዎ፤ ሔጀ ነበር፡፡ ያው! መቼም በአንዴ እሽ እንደማይባል አንተም ታውቃለህ፡፡ ለማንኛውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን ቀጥረውኛል፡፡ ቁርጡ ያኔ ይታወቃል" ::
"ቀጠሮ መስጠታቸውም ጥሩ ተስፋ ነው፡፡ እና እርሶንም በጣም አመሰግናለሁ"፡፡ ብሎ የማህበር ሰዓት ስለደረሰባቸው ወደየ ማህበራቸው ገቡ፡፡
አቶ ለማ ከማህበሩ እንደወጣ ወደ ቤቱ እየሔደ ፤ እንዴው እሽ ባለኝ፡፡ ልጅቷ ጎበዝ ተማሪ እና ጨዋ እንደሆነች መቼም አገር ነው የሚያወራላት፡፡ ፀባይዋም ቢሆን ምንም አይወጣላትም ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እንዴው በተሳካልኝ፡፡ ሰዎች ስለእድላዊት መልካምነት ሲያወሩ የሰማውን ሁሉ በሃሳቡ እየደጋገመ እና እያወራ ሳይታወቀው እቤቱ ደረሰ፡፡
"ምነው ዛሬ ደግሞ አመሸህ? ማህበሩ ቶሎ አላለቀም እንዴ?" አለ አበበ ላባቱ፡፡
"አዎ፤ ዛሬ ደግሞ ቶሎ ወደ ማህበር አልገቡም ነበር፡፡ ማህበረተኛውም የት እንደ ሄደ እንጃ ፤ጠላውም አላልቅ ብሎን እኔም ይመሽብኛል ብየነው ፤ ሳያልቅ ትቸው ነው የመጣሁት"፡፡
ከዛቲ መልስ ቄስ አሻግሬንም አግኝቻቸው ነበር፡፡ እቄስ መልካሙ ጋር እንደ ሔዱልኝ እና የድጋሜ ቀጠሮውም ለዛሬ አስራ አምስት ቀን እንደቀጠሯቸው ነገሩኝ" አለው፡፡
አበበ ለእድላዊት አማላጅ እንደላከለት ሲነግረው በጣም ወደር የሌለው ደስታ ተሰማው፡፡ ለማግባት የሚያስፈልገውን ነገር ማሟላት እንዳለበት በመወሰን የጀመረውን የቤት ስራ ለመጨረስ እየተጣደፈ ነው፡፡
እድላዊት ግን እሽ ትበለውም አትበለውም ባያውቅም ማድረግ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ባለበት ሰዓት በህሊናው አንድ ሃሳብ ያቃጭልበታል ?
ተመስገን
ሊነጋጋ ሲል የወሰደው እንቅልፍ ተጫጭኖት ቶሎ አልተነሳም፡፡ ለትምህርት ከሚነሳበት ሰዓት አርፍዶ ነው የተነሳው፡፡ የእድላዊት ባል ማግባት እና ከትምህርት መቅረት እውነት ሆኖ ቀረ ማለት ነው?፡፡ እውነት ባይሆንማ ኖሮ ሳትቀሰቅሰኝ ባልቀረች ነበር፡፡ ከራሱ ጋር እያወራ ከመኝታው ተነሳ፡፡ ሽንት ቤት ተፀዳድቶ ተመለሰ፡፡
እናቱን ከቤት ሲወጡ እበር ላይ አገኛቸው፡፡ እንደማይተዋወቅ ሰው የእግዚአብሔር ሰላምታ ሳይለዋወጡ ተላለፉ፡፡ የቤተሰቦቹ ድርጊት እና እርህራሔ የሌለው ውሳኔ ያስከፋው ተመስገን ለማነጋገር አይደለም የሚጨክን አንጀት እና አቅም ቢኖረው ቤተሰቦቹን በደበደባቸው ነበር፡፡
ወደ እድላዊት መኝታ ቤት አመራ፡፡ የቤቱ በር ከውስጥ የተዘጋ መስሎ ገርበብ ብሏል፡፡ እስካሁን ያልተነሳችው አሟት ቢሆን ነው፡፡ የቤቱን በር አንኳኳው፡፡ መልስ የሚሰጥ አላገኘም፡፡ ደጋግሞ በሩን ተመለከተ፡፡ ከነጋ የተከፈተ አይመስልም፡፡
ደግሞ ለማንኳኳት ሰውነቱን ከነከነው፡፡ ውስጡ ፍራት ፍራት ተሰማው፡፡ እጆቹም ተንቀጠቀጡ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ጠፋበት፡፡ ከውስጥ አልተዘጋ ይሆን እንዴ? ተጠራጠረ፡፡ በሩን ማንኳኳቱን ትቶ የሞት ሞቱን ገፋው፡፡ መዝጊያው ከውስጥ ምንም የያዘው ነገር ባለመኖሩ ተከፈተ፡፡ በፍርሃት ወደ ውስጥ ገባ፡፡
ከአልጋ በስተቀር እድላዊት አይደለችም ፤ የእድላዊት ልብስ እንኳን አላገኘም ነበር፡፡ የህሊና ፀሎት እንደሚያደርስ ሰው ቆሞ የስልክ እንጨት መሰለ፡፡ ደቂቃዎች አልፈው ከወሰደው የድንጋጤ ሰመመን ባነነ፡፡ በቀጥታ ወደ እናት አባቱ ቤት ሄደ፡፡ እድላዊትን የት ሄደች ? ብሎ እናቱን ጠየቀ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች የሚናገሩት ፣ የሚያነሱት ፣ የሚቧጥጡት አጡ፡፡ የት ሔደች? የለችም መኝታዋ ላይ ፤ እንደፎከረችው አደረገችው ማለት ነው፡፡ ወይ ጉዴ! እያሉ ከተመስገን መልስ ሳይጠብቁ ኡኡታቸውን አቀለጡት፡፡
የአካባቢው ሰውና ጎረቤቱ ምን ደረሰባቸው? ምን አጋጥሟቸው ይሆን?፡፡ እየተሯሯጡ ግቢው ሰው በሰው አጥለቀለቁት፡፡ታዲያ የሰው መዓት ቢሰበሰብ እና እሪ እየተባለ ቢጮህም እድላዊት ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ኡኡታ
ሰምተው ከመጡት ሰዎች መካከል ወ/ሮ ስንዱ "የት ትሔዳለች ፤ ከዚህ በፊት ከቤት ወጥታ አታውቅም፡፡
ወደ ዘመዶቿ ሔዳ ይሆናል፡፡ ሰው ልኮ ማጠያየቅ ነው" አሉ፡፡
ወ/ሮ አሰገደችን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ወ/ሮ አሰገደች ግን የሚረጋጉ አይደለም፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ነበር የሚመስሉት፡፡
ቄስ መልካሙ በድንጋጤ የተነሳ የሚጮኸውን ጩኸት የራሳቸው ችግር አይደለም፤ ለተመለከታቸው ሰው ከነጭራሹም ጩኸቱን የሰሙት አይመስልም ነበር፡፡
ጎረቤት የሆኑት አቶ ማን ችሎት ማን ያዝልሃል፡፡ ቄስ መልካሙን ለማነጋገር እና የተፈጠረውን ለመጠየቅ ቢሞክሩም ቄስ መልካሙ አይናቸውን ከማቁለጭለጭ ውጭ መልስ የሚባል ለመመለስ አይደለም ከነጭራሹም ለመናገር አቅቷቸው ነበር፡፡ ተመስገን ከእናት አባቱ የተሻለ ቢሆንም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ ግን እሱም መመለስ አልቻለም፡፡
የተሰባሰቡት ሰዎች ሁሉ የሚያደርጉት ጠፋቸው፡፡ ከመካከላቸው አንድ ሰው መኮንን ሃይሌ የሚባል ተነሳ
"አሁን ሁላችንም አብሮ ማጃበሩን እና ማልቀሱ ዋጋ ያለው አይመስለኝም፡፡ እነሱን አረጋግተን መላ ብንፈልግ የሚሻል ይመስለኛል፡፡ ብሎ ሃሳብ ሰነዘረ፡፡ የተሰበሰበው ሰው በሃሳቡ ተስማምቶ ወሮ አሰገደችንና ባለቤታቸውን አረጋግተው እድላዊትን ፍለጋ በየ አቅጣጫው ሁሉም ሰው ተበታተነ፡፡
እድላዊት ግን በዘመዶቿ ቤት አይደለም በዱር በገደሉም ልትገኝ አልቻለችም፡፡ ከጠፋችበት ቀን አንስቶ አየናት፡፡ በዚህ አልፋለች የሚል አይደለም የበላት ጅብ እንኳን ሊጮህ አልቻለም፡፡
ቄስ መልካሙ በልጃቸው መጥፋት ጥልቅ ሃዘን ተሰማቸው፡፡ እድላዊት ትሙት ትኑር ሳያውቁ "አይ! አንተ ሰማይ እና ምድርን የፈጠርህ ጌታ እንደዚህ በቁሜ እንዳዋረደችኝ እና እንዳሰቃየችኝ በቁሟ የሚያዋርድ ይስጣት፡፡ የፈጠሯትን ልጅ አምርረው ረገሟት፡፡
👍73❤4👏3
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡
የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡
መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡
ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡
መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡
እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡
ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡
ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡
እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡
እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡
እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡
ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡
"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡
እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡
እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡
አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?
እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;
እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡
እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡
ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡
እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡
ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡
እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡
አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
ከወሰዳት የንቅልፍ ሸለብታ ነቃች፡፡ መኝታዋን ሳታነጥፍ ለምን እንደተኛች ግራ ተጋባች፡፡ የሆነውን እና የተፈጠረውን ነገር ሁሉ ለማስታወስ አንድ በአንድ ወደ ኋላ ተመልሳ በሃሳብ ነጎደች፡፡
የተነሳችበት ሰዓት ሳይነጋ እኩለ ለሊት ላይ ነው፡፡ ወዴት እንደምትሔድ ጨነቃት፡፡ ልቧ ሸፍቶ ጥፊ እያለ አስቸግሯታል፡፡ ለመጥፋት ወሰነች፡፡
መተኛቷን ትታ ቁጭ አለች፡፡ ወዴት እንደምትጠፋ እና ወዴት እንደምትሔድ አሰበች፡፡ ምን ይገጥመኝ ይሆን ? እንደገና ደግሞ ሃሳቧ እየተቀያየረባት ከምጠፋ ታንቄ ብሞት አይሻልም ? ሰርጌን ለመብላት ሲያደገድጉ በአቋራጭ ተስካሬን ይበሉ ነበር፡፡
ሃሳቧን እየቀያየረች ስታወጣና ስታወረድ ቆየች፡፡ አልሸነፍም ፤ አልረታም ፤ ለሞት እጄን አልሰጥም ብሎ የመጥፋት መንገድን የመረጠው ልቧ ሳይመለስ ቀረ፡፡ ሲገፋፋት ቆየ፡፡ ልቧ የመጥፋት መንገድን ማሸነፍ አልቻለም፡፡
ከሔደችበት የሃሳብ ሰመመን ተመለሰች፡፡ ሌሊቱ እየነጋጋ ነው፡፡ የታጠበውንም ፣ ያልታጠበውንም ልብሷን በፌስታል ሸከፈች፡፡ ቤተሰቦቿ ሳይሰሟት መውጣት እንዳለባት ወሰነች፡፡
መጥፋትን የወሰነችው እድላዊት መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ጓዟን ጠቅልላ የእናት አባቷን ቤት እና የተወለደችበትን ቀዬ ለቃ ለመሄድ ተነሳች፡፡በሮቹን ድምፅ ሳታሰማ እና የተከፈቱ ሳታስመስል ግቢውን ለቃ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ጉዞዋን አሃዱ አለች፡፡
ትንሽ እንደተጓዘች ጨለማው እየለቀቀና እየነጋጋ ሄደ፡፡ እለቱ እሁድ በመሆኑ በሩቅ ርቀት ላይ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሔዱ ተመለከተች፡፡ የምትጓዝበትን መንገድ ትታ ሰው ሳያያት ለመሔድ ፈለገች፡፡ አማራጭ መንገድ በጫካ ውስጥ መረጠች፡፡ የአካባቢው ሰው እንዳያያት የጫካውን መንገድ ይዛ መጓዝ የግድ ሆነባት፡፡
እድላዊት ከቤት ስትወጣ ከልብሷ በስተቀር የሚበላ ስንቅ አልያዘችም፡፡ በጉዞው አድካሚነትና አሰልችነት የተነሳ እራባት፡፡ ውሃም እየጠማት መጣ፡፡ ምግብ የበላችበትን ሰዓት አስታወሰች፡፡ ከትምህርት ቤት ከወንድሟ ጋር ስትመጣ የቀመሰች ነው፡፡ እራትም ሳትበላ ነበር ያደረችው፡፡
ድካሟ እየባሰባት መጣ፡፡ አረፍ ለማለት በምትጓዝበት ጫካ ውስጥ ወደ ሚገኝ አንድ ትልቅ ዛፍ ስር ተቀመጠች፡፡ ውሃ ጥሙ ግን እየባሰባት ሄደ፡፡ ካረፈችበት ዛፍ ስር ተነሳች፡፡እየተጓዘች በአይኖቿ መንደር እና ውሃ በአካባቢው እያፈላለገች ፣ እየቃኘች ስትሔድ ጫካ ከመሆኑ አንፃር ውሃና መንደር የሚባል በቅርብ ልታገኝ አልቻለችም፡፡ ታዲያ ማፈላለጓን አላቋረጠችም፡፡ ከምትሄድበት መንገድ ባሻገር ከብቶች ሲሔዱ ተመለከተች፡፡
ከብቶቹ ወደ ውሃ እንደሚሄዱ ገመተች፡፡ የያዘችውን መንገድ ለቃ ከብቶቹ የሚጓዙበትን መንገድ በመያዝ ተከተለች፡፡
እውነትም የገመተችው ትክክል በመሆኑ ከብቶቹ ውሃ ሲጠጡ አገኘቻቸው፡፡
እድላዊት የጠማትን ውሃ ለመጠጣት ከብቶቹ ከሚጠጡበት ከፍ ብላ ልትጠጣ ተቀመጠች፡፡ የሚያንጎራጉር እና የፉጨት ድምፅ ሰማች፡፡ውሃውን ሳትጠጣ የሚያንጎራጉረውን የሰው ድምፅ ከየት አቅጣጫ እንደሆነ ለመለየት በአይኖቿ አማተረች፡፡
የእንጉርጉሮው ድምፅ እየቀረባት መጣ፡፡ ፍራት ፍራት ተሰማት፡፡ የዛሬን አውጣኝ ከዚህ ጫካ እያለች ፈጣሪዋን እየተማፀነች ፤ እየተርበተበተች አብዝታ ለመነች፡፡
የሚያንጎራጉረው የእንጉርጉሮው ድምፅ ከብቶች የሚያጠጡ እረኞች ነበሩ፡፡
እድላዊት እረኞቹን ፈራች፡፡ የመውጫዋን እና የማምለጫ መንገዷን ፈለገች፡፡
ከብቶቹን ከሚያጠጡት ሁለት እረኞች መካከል አንዱ ከበደ የሚባለው እረኛ እያንጎራጎረ ወደ ወንዙ ቀና አለ፡፡ አንድ የተቀመጠ ሰው ተመለከተ፡፡
ለጓደኛው ደበበ ያየውን ሰው ያ ማነው ? እዛ ላይ የተቀመጠው? አለ፡፡ ደበበ ጓደኛው እንዳለው ወደ ላይ ቀና ብሎ አየ፡፡ ቁጭ ያለ ሰው ተመለከተ፡፡
"ውሃ የሚጠጣ ሰው ይሆናል" አለው ለጓደኛው፡፡
እድላዊት እረኞች በእጃቸው እየተጠቋቆሙ ሲመለከቷት የባሰ ፈራች፡፡ በድንጋጤ እንደጠማት ልትጠጣ በእጇ የጨለፈችውን ውሃ እንኳን ሳትጠጣ ተነሳች፡፡ ቁጭ ብላ ከእረኞቹ ማምለጫ ስታማትር ወደ አገኘችው መውጫ መንገድ ተነስታ ለማምለጥ ሞከረች፡፡
እረኞቹ እድላዊትን ወንዝ ላይ ተቀምጣ ሰው ከመሆኗ ውጪ ወንድ ይሁን ሴት ትሁን አላወቋትም ነበር፡፡
እድላዊት ውሃ ለመጠጣት ከተቀመጠችበት ተነስታ ስትሮጥ ተመልክተው ሴት መሆኗን ለይዋት ፤ ከብቶቻቸውን ማጠጣታቸውን ትተው በእድላዊት መልክና ውበት እየተገረሙ በአይናቸው ተከትለው ሸኟት፡፡
አይን ለአይን እየተያዩ፡፡ የማነች ቀሽት ባክህ! ስታምር ፤ ከየት ይሆን የምትመጣው?
እውነትም ቀሽት ናት፡፡ ደግሞ እየፈራች ነው ፣ የምትሔደው፡፡ ምን ያገላምጣታል;
እረኞቹ እድላዊት ስትርበተበት አይተዋት ፤ ብቻዋንና የተከተላት ሰው አለመኖሩን ነቅተውባታል፡፡ይች ቀሽት ሳታመልጠን እንከተላት ተባባሉ፡፡ መጀመሪያ በአይናቸው ሸኝተዋት ቢመለሱም ልባቸው ግን ተከትሏት ነበር፡፡ እየተጣደፉ
እንዳታመልጣቸው በሔደችበት መንገድ ተከተሏት፡፡ እድላዊት የልቧ ትርታ ጨመረ፡፡ ሰውነቷ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ አለ፡፡ ይከተሉኝ ይሆን ብላ ተጠራጠረች፡፡ እንዴው አምላኬ
የዛሬን አውጣኝ፡፡ ከዚህ ከጨለማ፡፡ እያለች እንዳይደርሱባት በደከመ አቅሟ ለመሮጥ ሞከረች፡፡ ለእሷ የሮጠች መሰላት፡፡ ዳገቱ ግን ሊገፋላት አልቻለም፡፡ መልሶ ወደ መጣችበች ይገፈትራት ነበር፡፡ በአይኖቿ ወደ ኋላ፤ እየተመለሰች ብትገላመጥም የጠረጠረችው እና የፈራችው አልቀረም ፡፡ ባልጠበቀችው አቅጣጫ ሁለቱም እረኞች ከላይ እንደመጣ የመብረቅ ነበልባል ሆነው ደረሱባት፡፡
እድላዊት መሬት ተከፍታ ብትውጣት እንዴት በተደሰተች ነገር፡፡ ግን መሬት ተከፍታ ልትውጣት አልቻለችም፡፡ በድንጋጤ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ ላብ በላብ ሆነች፡፡ እረኞቹ ግን የሚተዋትና የሚያዝኑላት አይመስሉም፡፡
ገና ሳይዟት ከነ ነብሷ የሚውጧት ነበር የሚመስሉት፡፡ አንበሳ አፍ ውስጥ እንደገባ ስጋ እንደሆነች ታወቃት፡፡
እረኞቹ ከመንገድ ላይ እጆቿን ይዘው ወደ ጫካ ጎተቷት፡፡ ማምለጥ አልቻለችም፡፡ ነብስ ዝም ብላ ከስጋ እስከ ምትለይ መፈራገጧን አተውም እና እድላዊትም እየጮኸች ባላት አቅም እየተፈራገጠች ጩኸቷን አባረቀችው፡፡
ዘመድና ወገን እንደሌላት መሬት ለመሬት ነብሱ እንደወጣ የአህያ እሬሳ ጎተቷት፡፡ ያ የሚያምረው ለግላጋና ማራኪ ውበቷ በደምና በአቧራ ተለወሰ፡፡
ከሴት ልጅ እንዳልተፈጠሩ እናትና ሴት እህት እንደሌለው ሰው ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ድርጊት ለወሷት፡፡ መንገዱን አስለቅቀው ጫካው ውስጥም አስገቧት፡፡
እግዚአብሔር የእድላዊትን ስቃይና መከራዋን አይቶ ፤ የመማፀኒያ ልመናዋን ሰምቶ ፤ መላክተኛውን የሚካኤል አምሳያ ላከላት፡፡
አደን እንኳን ወጥቶ አያውቅም፡፡ አቶ አርምዴ የሚባል ሚንሻ፡፡ እድላዊት በአረመኔዎቹ እረኞች ተይዛ በምጮህበት በረሃ አካባቢ ነበር፡፡ አንድ አሳቻ ቦታ ተቀምጦ የሚያድነውን አውሬ እየፈለገ፡፡ በጫካው ውስጥ የሴት ልጅ ጩኸት ሰማ፡፡ ተነስቶ ወደ ጩኸቱ እሮጠ፡፡ ሁለት ልጆች እድላዊትን መሬት ለመሬት እየጎተቷት ደረሰ፡፡
👍86❤7🔥1👏1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ተመስገን
ከጠፋች በኋላ፤ ብቻ ሳይሆን ከእድላዊት ጋርም ከትምህርት ቤት መጥተው ምሳቸውን ከበሉበት ቀን አንስቶ ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አይደለም አስቦትም አያውቅም፡፡
ወደ ትምህርት ቤትም አልሄደም፡፡ ትዳር የሚባል ሳያስብ እናት አባቱን እየረዳ የግብርና ስራውን ሌት ከቀን እየተጋ መዋሉን ተያይዞታል፡፡
ከሚወዳት እህቱ እድላዊት ውጪ የቅርብ ጓደኛዬ የሚለው ሴትም ይሁን ወንድ ለግዜው አልነበረውም፡፡ አንድ ቀን በስራ ምክንያት ከሰፈሩ ልጅ ያሬድ ጋር ይገናኛል፡፡ ታዲያ ተመስገንና ያሬድ ከዚህ በፊት ከእግዚአብሔር ሰላምታ በስተቀር የጠበቀ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡
ያሬድ ተመስገንንም ይሁን ቤተሰቦቹን በደንብ ጠንቅቆ ያውቃቸዋል፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ያደገና ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖር ገና ታዳጊ ወጣት ሆኖ በራሱ ፈቃድ
ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ግብርናው ከተሰማራ ሰንበትበት ብሏል፡፡
ከተመስገን ጋር ግንኙነታቸው ከእግዚአብሔር ሰላምታ አልፎ ወደ መቀራረብ ደረሰ ፤ አልፎ አልፎም ስራ በመተጋገዝ መረዳዳት ጀምረዋል፡፡
ተመስገን እንደ እህቱ የሚሆንለት ባያገኝም ለእሱ የሚሆንና የሚያበረታታው የቅርብ ጓደኛ በማግኘቱ ደስተኛ አድርጎታል፡፡
ከእለታት አንድ ቀን እነያሬድ ቤት የሽንብራ ቆሎ እየፈጩ ፤ ከስንዴው ጠላ ጎንጨት እያሉ የወደፊት ምኞታቸውና አላማቸውን ይጫወታሉ፡፡
"ለወደፊት ምን ለመስራት አስበሃል?" ብሎ ጠየቀው ተመስገን፡፡
"እኔ ለቀጣይ ያስብኩት አሁን የጀመርኩትን ቤት ስጨርስ ቤተሰቦቼ ትምህርትህን ከተወህ ማግባት አለብህ እያሉኝ ስለሆነ ለማግባት አቅጃለሁ፡፡ ብሎት አንተስ ምን አስበሃል? አለው ያሬድ፡፡
ተመስገን የወደፊት ምኞትና እቅዱ ከጓደኛው ያሬድ የተለየና ተቃራኒ ነው፡፡ "እኔ እንኳን እህቴን እስከማገኝ ድረስ ትዳር የመያዝ ሃሳብና ፍላጎት የለኝም"፡፡
ቤተሰቦቸን እየረዳሁ ለራሴም ትንሽ እያጠራቀምኩ ለመኖር ነው የማስበው አለ፡፡
ያሬድ የተመስገንን እቅድ ሲሰማ እህቱን በፊትም እደሚወዳት ስለሚያቅ ለምን አታገባም ብሎም አልጠይቀውም..፡፡
አርምዴ
ባለቤታቸው ከሞተ በኋላ፤ ሌላ ባል አላገቡም፡፡ ወደ ውጭ ወጥተው ጎንበስ ቀና ብለው መስራት አይችሉም፡፡
ልጃቸው ሰርቶ የሚሰጣቸውን እህል አብስለው ለመብላት ያልተቸገሩ የስልሳ ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ የአርምዴ እናት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ቀኑ እንደመምሸት ብሎ ለዓይን ያዝ አድርጓል፡፡ ኩራዝ ለመለኮስ ከምድጃቸው እሳት ለማቀጣጠል ይታገላሉ፡፡
አይናቸው ተርገበገበባቸው፡፡ ዛሬ ደግሞ በምሽት ምን ሊያሳየኝ ነው ፡፡ አይኔ የሚርገበገበው እያሉ የውጭ በር ተንኳኳ
እሳት ማቀጣጠሉን ተወት አርገው ወደ ውጭ ወጡ፡፡ ልጃቸው አርምዴ እድላዊትን አዝሎ ገባ፡፡ ደነገጡ፡፡
"ውይ! በሞትኩት ልጄ ምን ሆና ነው? ብለው ጠየቁት፡፡
እረኞች ጫካ ውስጥ መሬት ለመሬት ጎትተዋት ነው፡፡
"እና በጣም ጎድተዋታል" ?
"አዎ! ይዣትም ስመጣ ለማናገር ብሞክርም ማናገር አልቻለችም"፡፡
"ታዲያ ከየት እንደመጣችም አልነገረችህም"?
"አልነገረችኝም ፡፡ ጩኸት ሰምቼ እየሮጥሁ ሲሄድ ጥለዋት ተበታተኑ፡፡ እሷም ተጎድታ ስለነበር አላናገረችኝም፡፡ እንዴው እግዚአብሔር ድረስላት ሲለኝ ነው እንጂ ዛሬ አደን የሔድኩት ይገሏት ነበር፡፡
"አሁን ምን እንስጣት? ነው ትንሽ ትተኛ? ድካሟ እስከ ሚያልፍላት አሉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
ወደ አስተኛት ፍራሽ ላይ ተጠጋ፡፡ እድላዊት አይኖቿን አንከራተተች፡፡ ግራና ቀኝ ተቁለጨለጨች፡፡
አርምዴ የእድላዊትን አይኖች መንከራተትና በእንባ መሞላት አየ፡፡ እሱም ከየት መጣ ሳይባል አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡
እድላዊት አርምዴን የምትመለከተው ውሃ ስጠኝ ለማለት ነበር፡፡ ግን መናገር አቅቷታል፡፡
አቶ አርምዴ ውሃ መፈለጓን የተረዳት አይመስልም፡፡ አንጀቱ እንደነብሰጡር ተላወሰ፡፡ እንባ እየተናነቀው "ምን ልስጥሽ " አላት፡፡
እድላዊት መናገር አልቻለችም፡፡ በእጇ ውሃ እንደ ጠማት አመለከተችው፡፡
አቶ አርምዴ በምልክት የገለፀችውን ሳያደናግረው ተረዳት፡፡ ውሃ ቀድቶ ሰጣት፡፡
ውሃው ወደ ውስጥ መግባቱን ትቶ ግራና ቀኝ በአፏ ወደ ውጭ ፈሰሰ፡፡
እድላዊት በውሃ ጥም የተነሳ ቶንሲሏ ወርዷል፡፡ አቶ አርምዴ የባሰ ተጨነቀ
"ውይ በሞትኩት ልጄን ውሃ አልወርድላት አለ ? ቶንሲሏ ወርዶ ይሆናል አሉ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"እና ምን ይሻላል? መድሃኒት በቅርብ አይገኝም? አለ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የሃበሻ መድሃኒት ሊያቀምሷት መድሃኒቱን እንዲያመጣላቸው ልጃቸውን እንዳይልኩት መድሃኒቱ ሲቆረጥ ስሙ መጠራት የለበትም፡፡ እራሳቸው ለመቁረጥ ቆይ እስቲ መጣሁ ብለው ወደ ጓሮ ሄዱ፡፡
ለቶንሲል መድሃኒት የሚሆነውን ሰባት የጌሾ ቀንበጥ ቆርጠው አመጡ፡፡ ለእድላዊት እንድታኝከው ሰጧት፡፡
እድላዊት መናገር ቢያቅታትም መስማት ትችላለች፡፡ የተሰጠችውን የቶንሲል መድሃኒት አኝኪው ስለተባለች ብቻ
እየመረራት ቢሆንም ጨክና አኘከችው፡፡
በውሃ ጥም ምራቋ ደርቋል፡፡ ከንፈሮቿም ኩበት መስለዋል፡፡ ምላሷ ብቻ ብቅ ጥልቅ ይላል፡፡ ነብሷ ልትወጣ ደረሰች፡፡ ሰውነቷ በላብ ተዘፈቀ፡፡ ልቧ ተጨነቀች፡፡ በጀመረችው የምልክት ቋንቋ ውሃ ስጡኝ ብላ በእጇ አመለከተች፡፡
አቶ አርምዴ የእድላዊት ነገር አሁንም ግራ ገባው፡፡ ከሸንበቆ ላይ ቀጭን ሸንበቆ ተከርክሞ እድላዊት በሸንበቆው አማካኝነት ውሃ እንድትቀምስ ተደረገ፡፡
ለእድላዊት እንጀራ እንዳይሰጧት ችላ አትበላም፡፡ ምን እንደሚሰጧት ጨነቃቸው፡፡ የእድላዊት ነገር አንጀታቸውን በላው፡፡
በደከመ አቅማቸውም ቢሆን ትንሽ ገንፎ አገንፍተው እንድትቀምስ አደረጉ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
እድላዊት የተሰራላትን ገንፎ ለመድሃኒት ያህል ቀመሰች፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ለቶንሲሏ ሌላ መዳኒት ዝንጅብል እንድታኝክበት ሰጧት፡፡
"ለቶንሲል ጥሩ ነው፡፡ ለነገ በደንብ ይሻልሻል፡፡ አይዞሽ እያሉ ልጃቸው ያሰረላትን ጨርቅ ከቁስሏ ላይ ፈቱላት፡፡ ለብ ባለ ውሃ አጠቡላት፡፡ ያበጠውን እግርና እጇንም በቅባት አሹላት፡፡ የተላላጠውን ቁስሏንም በነጠላ ጨርቅ ተኩሰው መኝታ ላይ ጋደም እንድትል አደረጉ፡፡
አቶ አርምዴ የሚደረግላትን ካደረገ በኋላ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ አድሮ በነጋታው ጥዋት እድላዊት እንዴት እንዳደረች ለመጠየቅ ከመኝታው ተነስቶ ሲመጣ እናቱ የቤቱን በር ከፍተው ሲወጡ ደረሰ፡፡
የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋውጠው "ደግሞ ማታ እመለሳለሁ ብለህ ሳትመጣ ቀረህ በሰላም ነው ያልተመለስከው? አሉት ወ/ሮ በሰልፏ፡፡
"ለመምጣት አስቤ ነበር፡፡ ግን ቤቱንና ከብቶቹን ትቼ እንዳልመጣ አውሬ እንኳን ቢገባ የሚሰማ ስላልነበረ ቀረሁ"፡፡ እንዴት አደረች ልጅቷ?ተሸሏት አላደረችም? አለ፡፡
የእድላዊት ስቃይና መከራ ከአንጀቱ ገብቶ ሳይወጣ አንጀቱ እያለቀሰላት እህል እንኳን አልወርድ ብሎት ለአደን ሲሄድ በቀመሰው ቁራሽ እንጀራ ነበር፡፡ እራት ሳይቀምስ ያደረው፡፡
ከአሁን አሁን ያማት ይሆን ? እያሉ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው አይደለም በዓይናቸው ሳይዞር ነበር ያደሩት ወ/ሮ በሰልፏም፡፡
"ሰላም አድራለች፡፡ ብቻ ሌሊቱን ሲያቃዧት ነው ያደረው፡፡ አሟት ይሆን ብየ ሌሊት ተነስቼ ሳያት ከቅዠት በስተቀር ምንም አላየሁባትም፡፡ ከነጋም አልቀሰቀስኳትም፡፡ ቅዝቃዜ ስላለ ትንሽ ትተኛ ብየ ነው፡፡ እስኪ አሁን አንተ ከመጣህ ቀስቅሳትና እንዴት እንዳደረች ጠይቃት አሉ፡፡ ቤታቸውን ለመጥረግ የቤት መጥረጊያ ቅጠል ለማምጣት ወደ ውጭ እየወጡ፡፡
👍88❤10🥰3👎1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
#ያሬድ
ሁሉም ተሳካለት፡፡ ከዚያው አካባቢ አበበች የምትባል ልጅ አገባ፡፡ ኑሮውን ለማሻሻል ከግብርና ስራው በተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት አቀደ፡፡ ለባለቤቱ ማማከር እንዳለበት ወሰነ፡፡
አንድ ቀን ከባለቤቱ ጋር እራት እየበሉ ነው፡፡ "እንዴው ይሔ የግብርና ስራ ከእጅ ወደ አፍ ብቻ ሆነ፡፡ በትርፍ ሰዓቴ እንኳን ንግድ ብሞክር ፤ ሳይሻል አይቀርም" አላት ያሬድ ለባለቤቱ አበበች፡፡ በእጁ የተቀለለውን እንጀራ እየጎረሰ፡፡
"ሃሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን ምን ዓይነት ንግድ ነው የምነግደው? አለች አበበች፡፡
ጥያቄን በጥያቄ እንዲሉ መልሶ "ቡና ይሻላል ወይስ አልባሳት?'' አላት፡፡
ሁለቱም አማራጮች ጥሩ ናቸው፡፡ ግን ከየት አምጥተህ ነው የምትነግደው ?፡፡
ያሬድ ተጨማሪ የንግድ ስራ ለመስራት እንጅ ከየት አምቶ እና ምን እንደሚነግድ እንኳን በደንብ አላሰበበትም፡፡
አልባሳት በቅርብ ባይገኝም ወደ ድሬደዋ በመሔድ ማግኘት እንደሚቻል ግን ያውቃል፡፡
"ድሬደዋ በውሎ ገባ መድረስ ይቻላል እንዴ"? አለችው፡፡
ያሬድ ድሬደዋ ሔዶባት አያውቅም፡፡ "ሰዎች ሲያወሩ ሰምቻለሁ፡፡ ውሎ ገባ አይደረስም፡፡ መኪና ከተገኘ ሁለት ቀን ቢወስድ ነው"፡፡
ያሬድ ከባለቤቱ ተስማምቶ ፤ ማምጫ ገንዘብ ለሰው አበድሮት የነበረውን ሰበሰበ፡፡ ከቤትም ትንሽ ስንዴ ሸጦ ለመነገጃ የሚሆን ገንዘብ አጠራቀመ፡፡
ታዲያ ወደ ድሬደዋ ሲሔድ ቤቱን ፣ ከብቶቹንና ባለቤቱን ብቻዋን ጥሏት እንዳይሄድ ስጋት አደረበት፡፡
ተመስገን ለቤተሰቦቹ ውሃ ሊቀዳ አህያ ላይ ጀሪካን እየጫነ ነው፡፡
"ደህና አደርህ ተመስገን" አለ፡፡ ቤቱን እና ከብቶቹን እስከሚመለስ እንዲያይለት ሊጠይቀው በጥዋት የመጣው
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ያሬድ" አለ፡፡ ጀርካን መጫኑን ተወት አድርጎ ወደ ያሬድ እየተጠጋ፡፡ የእጅ ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ቤት ግባ አለው ተመስገን፡
"አልገባም ይሁን" ብሎ "አንተጋር ነበር የመጣሁት" አለ
"ምነው በሰላም" ?
"አይ! በሰላም ነው፡፡ አንድ ነገር ላስቸግርህ ብየ ነው የመጣሁት"፡፡
"ምን ችግር አለው የምችል ከሆነ"፡፡
"አይ! ቀላል ነው"፡፡ እኔ ወደ ድሬደዋ ለመሄድ ስለፈለግሁ ቤቴን እንድትከታተልልኝ ፈልጌ ነበር፡፡
"ምነው በሰላም ነው፡፡ ወደ ድሬደዋ የምትሄደው ?
"ለራሴ ጉዳይ ነው፡፡ ትንሽ አልባሳት ለመነገድ ስላሰብኩ ለማምጣት ነው የምሔደው ፡፡
"አይ! ደህና ነው፡፡ እከታተልልሃለሁ ግን ለምን አብረን ብቻህን እዛ ድረስ ከምትሄድ ለኔም ታስተዋውቀኝ ነበር አለ ተመስገን፡፡
"ሐሳብህ ጥሩ ነው፡፡ ግን እኔም ገና አዲስ ስለሆንኩ መጀመሪያ ልየውና የሚያዋጣ ከሆነ አብረን እንሔዳልን እስከዛ ገንዘብ አጠራቅም፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ተለያያዩ።
እድላዊት
ሲሻለኝ ውለታቸውን በጉልበቴም ቢሆን አግዠ እከፍላቸዋለሁ ብላ አሰበች፡፡ ግን ያሰበችው ቶሎ አልሆነም፡፡
ከህመሟ ሳይሻላት እየባሰባትና እየጠናባት ሄደ፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ ሆና አሳለፈች፡፡ ምነው እዛው ጫካ ሞቼ በቀረሁ ኖሮ፡፡ እንደዚህ የአልጋ ቁራኛ ሆኘ ሰው ከማስቸገር ምን አለ ፈጣሪየ መከራና ስቃየን ከምታበዛብኝ ብትገላግለኝ?፡፡ ፈጣሪዋን እየተማፀነች እና እያማረረች ውላ በተራው ጨለማውን ተገን አድርጎ ሌሊቱ ይተካል፡፡
እድላዊት ሌሊትም ሆነ ቀን የምትተኛበት የእንቅልፍ ሰዓት በሃሳብና በጭንቀት ሳይታወቃት ቀን መሽቶ ይነጋል፡፡ በብርድልብስ ውስጥ ተሸፍና የምታለቅሰው እንባ ቢጠራቀም ዘመዶቿንና ቤተሰቦቿን ይቀብርላት ነበር፡፡
አንዳንዴ ሲጨንቃት የተሻላት ይመስላታል፡፡ ለመሄድ አስባ ትነሳለች፡፡ አሁን ልሂድ በቃ ተሸሎኛል፡፡ እናንተንም
አስቸገርኳችሁ፡፡ ተነስታ ለመሄድ ስታስብ አቅም ያንሳታል ፤ እራሷን ያዞራታል፡፡ ተመልሳ መቀመጥ አትችልም፡፡
የእድላዊት ቶሎ አለመዳንና የአልጋ ቁራኛ መሆኗ አሳስቧቸዋል ፤ ወ/ሮ በሰልፏ፡፡ ምነው ፈጣሪዬ ይህችን አንድ ፍሬ ህፃን የአልጋ ቁራኛ ከምታደርግብኝ ለኔ ብሰጠኝ፡፡ እያሉ ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ውለው ማደራቸው ሳያንሳቸው እድላዊት ደግሞ በሽታዋን ሳታስብ አስቸገርኳችሁ ስትላቸው የባሰ ያስጨንቃቸዋል፡፡
እባክሽን ልጄ ተለመኝኝ ; እባክሽ ስለፈጠረሽ አምላክ ; በደንብ ሲሻልሽ ትሔጃለሽ፡፡ ልጄ እባክሽ ለኔ ምንም አታስቢ፡፡ አንቺ ብቻ ዳኝልኝ፡፡ ለሁሉም ይደረሳል፡፡ ብለው ምንም እንዳታስብና እንዳትጨነቅ ይማፀኗታል ፡፡
እድላዊት በትንሹም ቢሆን እየተሸላት መጣ፡፡ መጀመሪያ ውለታቸውን ከፍየ እሄዳለሁ ብላ ያሰበችውን አረሳችም፡፡
ገና በደንብ ሳይሻላት ለመርዳት ተቻኮለች፡፡ ቡና ሲያፈሉ እኔ አፈላለሁ እያለች ወ/ሮ በሰልፏን ታስቸግራቸውም ጀመር፡፡ ቆይ በደንብ አልተሻለሽም፡፡ በደንብ ሲሻልሽ ታፈያለሽ፡፡ ቢከለክሏትም እሽ አትላቸውም ነበር፡፡
እድላዊት በቤቱ ውስጥ ያለውን ስራ በመስራት መርዳትና ማገዝ ጀመረች፡፡ ትንሽ ሲሻለኝ እሄዳለሁ ያለችውን ሰረዘች፡፡ ውለታቸውን በደንብ ለመክፈል ህሊናዋ አስገደዳት፡፡
የተባረከች ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነት ያደረባት፡፡ የትንሽ አዋቂ በማለት ያመሰግኗትም ነበር ፤ ወሮ በሰልፏ፡፡
ከባለቤታቸው አንድ ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ያለመታደል ሆኖ ግን ሁለቱን ሴት ልጆቻቸውን በአንድ ወቅት በተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ በሞት ተነጥቀዋል፡፡
የሴትን ልጅ ጥቅም በደንብ ያወቁት በእድላዊት እንጅ በልጆቻቸውም አልነበረም፡፡ እርጅናቸው ገፋ ባይባልም በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ሞት በመከራ ላይ መከራ አሳልፈዋል፡፡ አቅማቸው እየደከመ ፤ ጤንነታቸው ከቀን ቀን እየባሰባቸው ሄደ፡፡ የጤና ማጣታቸው ታዲያ አልጋ እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡
እድላዊት ከቤተሰቦቿ የተፈጠረችበትን ቀን ስታስታውስ አምርራ ትረግማለች፡፡ ቤተሰቦቿ እንደ ወ/ሮ በሰልፏ ቅን ፤ የሰውን ሃሳብ የሚረዱ ቢሆኑ ኖሮ ዛሬ ትምህርቷን ጨርሳ እሩቅ የመድረስ ፤ አላማዋና ተስፋዋ በተሳካላት ነበር፡፡
አንዴ ለመከራ የታደለች አድርጎ የፈጠራት እድላዊት፡፡ ከአልጋ ቁራኛ ተነስታ ውለታቸውን በጥቂቱም ቢሆን በጉልበቷ ከፍላ ለመሔድ ተነሳች፡፡ ግን አልተሳካላትም፡፡ ያስታመሟት ወሮ በሰልፏ ተረኛ የአልጋ ቁራኛ ሆኑባት፡፡
ጥላቸው እንዳትሄድ በእጃቸው በልታ ፣ ጠጥታ ያደረጉላት ውለታ ፤ መቼም የማይረሳ ሆነባት፡፡ ብትሔድ እንኳን የማይቀናትና የማይሳካላት መስሎ ታያት፡፡ ከስራቸው ሆና ለማስታመም ተገደደች፡፡
ወላጅ እናቷን እንደምጠራው እማዬ ምን ላምጣሎት ? ምን ላድርግሎት ? ምን ይሻላል ? እያለች አቅሟ የፈቀደውን ሁሉ እያደረገች አስታመቻቸው፡፡
ታዲያ ስትወጣና ስትገባ አይን አይናቸውን ስትመለከት ህመማቸው ፤ ህመሟ ይሆንባታል፡፡ ሁለት ወር ከ18 ቀን የአልጋ ቁራኛ እያለች
ያደረጉላት ሁሉ በሃሳቧ ይመጣ፡፡
አይኖቿ በእንባ ይሞላሉ፡፡ ስታለቅስ እንዳያዩዋት ወደ ውጭ ወጥታ ልውጣ ልውጣ እያለ በሃይል የሚያስቸግራትን ፤ የእንባ ጎርፍ ፊቷንና አይኖቿ እስከሚቀሉ ድረስ ታዘንበዋለች፡፡
ወ/ሮ በሰልፏ የራሳቸው በሽታና ስቃይ ሳያንሳቸው በእድላዊት ማሰብና መጨነቅ አንጀታቸው አልችል አለ፡፡
👍74❤6😁2🔥1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ደላላው
ያዋጣኝ ይሆን ? ወይስ ያከስረኝ ? ይሆን ? ተጠራጠረ ፤ የአልባሳት ንግዱ ግን ውጤታማ አድርጎታል፡፡ እየተመላለሰ መነገዱን ቀጥሏል፡፡
የባልጪ መኪና ቶሎ ያሬድ ወደ ድሬድዋ ሊሄድ ረፍዶበት ተቻኩሏል፡፡ መኪናው ግን ሳይሞላ መውጣት አልቻም፡፡ አዳማ አርፍዶ ደረሰ፡፡ ወደ ድሬደዋ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦታል፡፡
ተናደደ ፣ ተበሳጨ፡፡ ምነው ዛሬ ባልመጣሁ ኖሯል፡፡ እንደሚረፍድብኝ እያወቅሁ፡፡ ከባልጪ መመለስ ሲኖርብኝ፡፡ ወደ አዳማ መንከርፈፍ ምን ይሉታል? ራሱን እየወቀሰ ከአሰላ መውጫ መነሃሪያ ወጥቶ በስተቀኝ በኩል ወደ ምትገኝ አንድ ሻይ ቤት አመራ፡፡
አንድን ጠቆር ያለ ወጣት ነው፡፡ ቁመተ አጭር ዳክየ፡፡ የተከረከመ ጉቶ ይመስላል፡፡ ፀጉሩ በአቧራ የተለወሰ ፣ የተንጨበረረ ፣ ቁጥርጥር ፀጉራም፡፡
ከመነሃሪያ ውጭ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው የቀረው እያለ ይለፈልፋል፡፡
ቀኝ እግሩን አንስቶ ግራ እግሩን አልደገመም፡፡ ድሬ አንድ ሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ ወደ ፊት መራመዱን ትቶ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ብስጭትና ንዴቱ ለቀቀው፡፡ እየተጣደፈ ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው እያለ ወደ ሚለፈልፈው ደላላ ተጠጋ፡፡ እኔ አለሁ ድሬ አለ፡፡
"ኧረ! ድሬ ነህ ና ተከተለኝ፡፡ አሁን ልንወጣ ነው"፡፡ ብሎት ወደ መኪናው ወሰደው፡፡ ሂሳብ ክፈልና እዚህኛው መኪና ግባ አለው፡፡
ለመሳፈሪያ ብሎ ለይቶ ካስቀመጠው የሱሪ ኪሱ አውጥቶ ከፈለ፡፡ ደረሰኝ ግን አልተቀበለም፡፡ ደላላው ገንዘቡን ተቀብሎት ታጠፈ፡፡
ያሬድ ግባ ወደ ተባለበት አውቶቢስ ገባ፡፡ እውነትም አንድ ሰው ብቻ ነበር የቀረው፡፡ አንድ ተሳፋሪ ቀርቷት የነበረች ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡
እረዳቱ የአውቶቢሱን በር ዘጋ፡፡ ሹፌሩ መኪናውን አስነሳ፡፡ ጉዞው ከአዳማ ወደ ድሬደዋ ተጀመረ፡፡
"ምዕመናን ሂሳብ ወጣ! ወጣ! አድርጉ አለ እረዳቱ፡፡ እየተቀበለ ያሬድ ጋር ደረሰ፡፡
"ለእኔ ደረሰኝ ብቻ ስጠኝ ገንዘቡን ከፍያለሁ አለ ያሬድ፡፡
"ለማነው የከፈልከው አለ እረዳቱ?፡፡
"ሊያሳፍረኝ ይዞኝ ለመጣው ሰውየ ፡፡
"አባት የከፈሉት ሂሳብ ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ አሁን ለእኔ ይክፈሉኝ አለ፡፡ ትህትና በተሞላበት ንግግር፡፡
"አልከፍልም" አለ ያሬድ፡፡
"እባክዎት ይክፈሉኝ" አባት ቢልም ፤ ምንም ቢል ያሬድ ሊሰማ አልቻለም፡፡ ክፈል ፣ ጭቅጭቅና ንትርኩ ተባባሰ፡፡ ሹፌር መኪናውን መንዳቱን አቆመ፡፡ በረዳቱና በያሬድ መሃል ጣልቃ ገባ
"ለምንድ ነው የማከፍለው? በነፃ ተሳፍረህ የምትሄደው የአባትህ ፈረስ አደረግከው አለ ሹፌሩ፡፡ በፊቱ ላይ የደም ስሮቹ ተወጣጠሩ፡፡
"የአባቴ ፈረስ ባይሆንም ገንዘብ ከፍየ ነው የተሳፈርኩት፡፡ ያጭበረበራችሁኝ እናንተ ናችሁ፡፡ በማስፈራራት ደግማችሁ ልታስከፍሉኝ ነው? አልከፍልም፡፡ ወደ ህግ እንሄዳለን እንጅ አለ ያሬድ፡፡
ከመኪናው ውስጥ ጎትተው አወጡት፡፡ ሊደበድቡት ተጋበዙ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ገላገሏቸው፡፡ ክርክሩና ንትርኩ አላቋረጠም፡፡
አቶ ላንቻ ባልቻ የሚባሉ ከያሬድ ጋር አንድ ወንበር ላይ አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጭቅጭቁ አበሳጭቷቸዋል፡፡ ቶሎ ለመድረስ ያሰቡበት ቦታ እየረፈደባቸው ነው፡፡
"ለረዳቱ በቃ! ተወው እኔ እከፍለዋለሁ፡፡ ንትርኩን ተውና ቶሎ ቶሎ ንዳ፡፡ እውነት ይሄ ሰውዬ ሳይከፍልም የተከራከረ አይመስለኝም፡፡ የአዳማ ሞጭላፋ ጩልሌዎች ጨልፈውት ይሆናል፡፡ እንኳን የክፍለ ሃገር ሰው አግኝተው አይደለም ወፍ ከሰማይ ያወርዳሉ፡፡ ይዞት የመጣው ደላላ የሻይ ሲጠይቀው የመሳፈሪያውን ሂሳብ ተቀብሎት ላፍ ብሎ ይሆናል፡፡ ብለው የሚያጨቃጭቀውን የያሬድን ሂሳብ ከደረት ሸሚዝ ኪሳቸው አውጥተው ከፈሉለት፡፡
"አጭበርብረውኝ ነው፡፡ እንጅ እኔ እኮ ገንዘቡን ከፍያቸዋለሁ አባት አለ፡፡ እንደ መፀፀት ብሎ፡፡
"ያጭበረበሩህ ባለ መኪናዎቹ አይደሉም፡፡ ዱርዬዎች ናቸው፡፡ አንተም መኪና ውስጥ ሳትገባ መክፈል አልነበረብህም፡፡ ወይም ስትከፍል ደረሰኝ መቀበል ነበረብህ::
"እኔ መቼ አወኩ፡፡ እንደዚህ መሆኑን የት አውቄ፡፡ የእነሱ አጋዥ መስሎኝ ነው፡፡ የከፈልኩት፡፡ መቼ ሰባራ ሳንቲም አቀምሰው ነበር፡፡ ብሎ ስህተቱ የራሱ መሆኑን አውቆ የከፈሉለትን ገንዘብ ሊከፍል ከኪሱ አወጣ፡፡
አባት አመሰግናለሁ ገንዘቡን እንኩ አለ፡፡ በፊቱ ላይ የይቅርታ ምልክት እያሳየ፡፡
ገንዘቡን ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ ተወው ችግር የለውም፡፡ አንተም ተወስዶብህ ነው፡፡ እንጅ አውቀህ አይደለም፡፡ አሁን ያወጣኸውን ገንዘብ መልሰህ ወደ ኪስህ አስገባ እኔ አልቀበልም አሉ አቶ ላንቻ፡፡
አቶ ላንቻ ከድሬደዋ አዳማ እየተመላለሱ የሚነግዱ የታወቁ ቱጃር አልባሳ ነጋዴ ናቸው፡፡ ጨዋታቸው እየሞቀ ሄደ፡፡ አቶ ላንቻ ከተደገፉበት ወንበር ቀና አሉ፡፡
"ስምህን ማን አልከኝ"? አሉት፡፡ መጀመሪያ ነግሯቸው በጭዋታ የተነሳ ዘንግተውት ይሁን ተመስሎባቸው ደግመው መጠየቃቸው፡፡
"ያሬድ እባላለሁ አለ፡፡ ፊቱን ወደ አቶ ላንቻ መለስ አድርጎ፡፡
"አሁን ወዴት ነው የምትሄደው"? ፡፡
"ወደ ድሬ የምሄደው"፡፡
"እዛው ነዋሪ ነህ ወይስ ለስራ ነው የምትሄደው?፡፡
"አይ! ለስራ ነው፡፡ ነገ እመለሳለሁ፡፡ እቤት ከመቀመጥ ብዬ ትንሽ ሳልባጅ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡ ሞልቶ ለማይሞላ ነገር ስንት ገዛኸው ዘጠኝ ፤ ስንት ሸጥከው ዘጠኝ ፤ ትርፉስ ምንድነው? ዘጥ ዘጥ እንደሚባለው የበሰለውን ከማጥፋት ውጭ ድካም ነው፡፡ ውጤት የለውም አላቸው፡፡ ንግግሩ የሚያስቅ ስለነበር ፈገግ አደረጋቸው፡፡
አቶ ላንቻ አለመተዋወቅ እንጅ አልባሳት ከሆነ የምትነግደው እኔ አዳማ ድረስ አመጣልህ ነበር አሉ፡፡
"አልባሳት ይነግዳሉ እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"አዎ፤ ነጋዴ ነኝ፡፡ አሁንም አራግፌ እየተመለስኩ ነው፡፡
"ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ እንዴው የሰው መተዋወቂያው መንገዱ ብዙ ነው አለ ያሬድ፡፡ ያገናኛቸው አጋጣሚ እያስገረመው፡፡
"ድሬ ደንበኛ አለህ የምትረከብበት"? ፡፡
"ደንበኛ እንኳን የለኝም፡፡ የጀመርኩት ቅርብ ጊዜ ስለሆነ ደንበኛ አላበጀሁም፡፡ ከአሸዋ ሜዳ ነው የምገዛው ፡፡
የዛሬ መገናኘታችን ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ አሁን እየደረስን ስለሆነ መነሃርያ ሳንገባ ወርደን አረፍ ብለን እንነጋገራለን" አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
ከመኪና ወርደው ወደ አንድ ሪስቶራንት አመሩ፡፡ አረፍ ብለው የሚጠጣ ለስላሳ አዘዙ፡፡ በመኪና ላይ የጀመሩትን ጭውውታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
"አዳማ ውስጥ የራስዎ ቡቲክ አሎት እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"የራሴ እንኳን ቡቲክ የለኝም፡፡ አዳማ መነሃሪያ አካባቢ ቢያድግልኝ የሚባል የጅምላ አከፋፋይ ሱቅ አጠገብ የተከራየሁት ቡቲክ አለኝ፡፡ እዛ ነው የምሸጠው፡፡ ቦታውን ነገ አብረን ስንሄድ አሳይሃለሁ፡፡ አሁን እንሂድና እዚህ ድሬ ውስጥ ያለኝን ቡቲክ ላሳይህ፡፡ የሚያስፈልግህንም ገዝተህ እኔ በምጭንበት መኪና ጭነህ ነገ አብረን አንሄዳለን፡፡
ያሬድ ያገናኘውን አጋጣሚ እየመረቀ እንዴው ምን ዓይነት ደግ ሰው ነው፡፡ ያጋጠመኝ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ እያለ "አይደህና ነው፡፡ ለእኔም እዚህ ድረስ ከምለፋ ጥሩና መልካም ነው፡፡ እንዴው ውለታዎን ለመክፈል ያብቃኝ" አለ፡፡ ቀለስለስ እያለ፡፡
"አይ! ምንም ማለት አይደለም፡፡ የራሴም ስራ ነው፡፡ አሁን ከአንተ የምጠብቀው ታማኝ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው"፡፡ ብለውት ሊያሳድሩት ወደ ቤታቸው ወሰዱት፡፡
በነጋታው በጥዋት ተነሱ፡፡ በተነጋገሩት መሰረት የሚያስፈልገውን ልብሶች ገዝቶ አብረው ወደ አዳማ ተጓዙ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ደላላው
ያዋጣኝ ይሆን ? ወይስ ያከስረኝ ? ይሆን ? ተጠራጠረ ፤ የአልባሳት ንግዱ ግን ውጤታማ አድርጎታል፡፡ እየተመላለሰ መነገዱን ቀጥሏል፡፡
የባልጪ መኪና ቶሎ ያሬድ ወደ ድሬድዋ ሊሄድ ረፍዶበት ተቻኩሏል፡፡ መኪናው ግን ሳይሞላ መውጣት አልቻም፡፡ አዳማ አርፍዶ ደረሰ፡፡ ወደ ድሬደዋ በጥዋት የሚወጣው መኪና አምልጦታል፡፡
ተናደደ ፣ ተበሳጨ፡፡ ምነው ዛሬ ባልመጣሁ ኖሯል፡፡ እንደሚረፍድብኝ እያወቅሁ፡፡ ከባልጪ መመለስ ሲኖርብኝ፡፡ ወደ አዳማ መንከርፈፍ ምን ይሉታል? ራሱን እየወቀሰ ከአሰላ መውጫ መነሃሪያ ወጥቶ በስተቀኝ በኩል ወደ ምትገኝ አንድ ሻይ ቤት አመራ፡፡
አንድን ጠቆር ያለ ወጣት ነው፡፡ ቁመተ አጭር ዳክየ፡፡ የተከረከመ ጉቶ ይመስላል፡፡ ፀጉሩ በአቧራ የተለወሰ ፣ የተንጨበረረ ፣ ቁጥርጥር ፀጉራም፡፡
ከመነሃሪያ ውጭ ቆሞ አላፊ አግዳሚውን ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው የቀረው እያለ ይለፈልፋል፡፡
ቀኝ እግሩን አንስቶ ግራ እግሩን አልደገመም፡፡ ድሬ አንድ ሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡ ወደ ፊት መራመዱን ትቶ ወደ ኋላ ተመለሰ፡፡ ብስጭትና ንዴቱ ለቀቀው፡፡ እየተጣደፈ ድሬ ፣ ድሬ አንድ ሰው እያለ ወደ ሚለፈልፈው ደላላ ተጠጋ፡፡ እኔ አለሁ ድሬ አለ፡፡
"ኧረ! ድሬ ነህ ና ተከተለኝ፡፡ አሁን ልንወጣ ነው"፡፡ ብሎት ወደ መኪናው ወሰደው፡፡ ሂሳብ ክፈልና እዚህኛው መኪና ግባ አለው፡፡
ለመሳፈሪያ ብሎ ለይቶ ካስቀመጠው የሱሪ ኪሱ አውጥቶ ከፈለ፡፡ ደረሰኝ ግን አልተቀበለም፡፡ ደላላው ገንዘቡን ተቀብሎት ታጠፈ፡፡
ያሬድ ግባ ወደ ተባለበት አውቶቢስ ገባ፡፡ እውነትም አንድ ሰው ብቻ ነበር የቀረው፡፡ አንድ ተሳፋሪ ቀርቷት የነበረች ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡
እረዳቱ የአውቶቢሱን በር ዘጋ፡፡ ሹፌሩ መኪናውን አስነሳ፡፡ ጉዞው ከአዳማ ወደ ድሬደዋ ተጀመረ፡፡
"ምዕመናን ሂሳብ ወጣ! ወጣ! አድርጉ አለ እረዳቱ፡፡ እየተቀበለ ያሬድ ጋር ደረሰ፡፡
"ለእኔ ደረሰኝ ብቻ ስጠኝ ገንዘቡን ከፍያለሁ አለ ያሬድ፡፡
"ለማነው የከፈልከው አለ እረዳቱ?፡፡
"ሊያሳፍረኝ ይዞኝ ለመጣው ሰውየ ፡፡
"አባት የከፈሉት ሂሳብ ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ አሁን ለእኔ ይክፈሉኝ አለ፡፡ ትህትና በተሞላበት ንግግር፡፡
"አልከፍልም" አለ ያሬድ፡፡
"እባክዎት ይክፈሉኝ" አባት ቢልም ፤ ምንም ቢል ያሬድ ሊሰማ አልቻለም፡፡ ክፈል ፣ ጭቅጭቅና ንትርኩ ተባባሰ፡፡ ሹፌር መኪናውን መንዳቱን አቆመ፡፡ በረዳቱና በያሬድ መሃል ጣልቃ ገባ
"ለምንድ ነው የማከፍለው? በነፃ ተሳፍረህ የምትሄደው የአባትህ ፈረስ አደረግከው አለ ሹፌሩ፡፡ በፊቱ ላይ የደም ስሮቹ ተወጣጠሩ፡፡
"የአባቴ ፈረስ ባይሆንም ገንዘብ ከፍየ ነው የተሳፈርኩት፡፡ ያጭበረበራችሁኝ እናንተ ናችሁ፡፡ በማስፈራራት ደግማችሁ ልታስከፍሉኝ ነው? አልከፍልም፡፡ ወደ ህግ እንሄዳለን እንጅ አለ ያሬድ፡፡
ከመኪናው ውስጥ ጎትተው አወጡት፡፡ ሊደበድቡት ተጋበዙ፡፡ ተሳፋሪዎቹ ገላገሏቸው፡፡ ክርክሩና ንትርኩ አላቋረጠም፡፡
አቶ ላንቻ ባልቻ የሚባሉ ከያሬድ ጋር አንድ ወንበር ላይ አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጭቅጭቁ አበሳጭቷቸዋል፡፡ ቶሎ ለመድረስ ያሰቡበት ቦታ እየረፈደባቸው ነው፡፡
"ለረዳቱ በቃ! ተወው እኔ እከፍለዋለሁ፡፡ ንትርኩን ተውና ቶሎ ቶሎ ንዳ፡፡ እውነት ይሄ ሰውዬ ሳይከፍልም የተከራከረ አይመስለኝም፡፡ የአዳማ ሞጭላፋ ጩልሌዎች ጨልፈውት ይሆናል፡፡ እንኳን የክፍለ ሃገር ሰው አግኝተው አይደለም ወፍ ከሰማይ ያወርዳሉ፡፡ ይዞት የመጣው ደላላ የሻይ ሲጠይቀው የመሳፈሪያውን ሂሳብ ተቀብሎት ላፍ ብሎ ይሆናል፡፡ ብለው የሚያጨቃጭቀውን የያሬድን ሂሳብ ከደረት ሸሚዝ ኪሳቸው አውጥተው ከፈሉለት፡፡
"አጭበርብረውኝ ነው፡፡ እንጅ እኔ እኮ ገንዘቡን ከፍያቸዋለሁ አባት አለ፡፡ እንደ መፀፀት ብሎ፡፡
"ያጭበረበሩህ ባለ መኪናዎቹ አይደሉም፡፡ ዱርዬዎች ናቸው፡፡ አንተም መኪና ውስጥ ሳትገባ መክፈል አልነበረብህም፡፡ ወይም ስትከፍል ደረሰኝ መቀበል ነበረብህ::
"እኔ መቼ አወኩ፡፡ እንደዚህ መሆኑን የት አውቄ፡፡ የእነሱ አጋዥ መስሎኝ ነው፡፡ የከፈልኩት፡፡ መቼ ሰባራ ሳንቲም አቀምሰው ነበር፡፡ ብሎ ስህተቱ የራሱ መሆኑን አውቆ የከፈሉለትን ገንዘብ ሊከፍል ከኪሱ አወጣ፡፡
አባት አመሰግናለሁ ገንዘቡን እንኩ አለ፡፡ በፊቱ ላይ የይቅርታ ምልክት እያሳየ፡፡
ገንዘቡን ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ ተወው ችግር የለውም፡፡ አንተም ተወስዶብህ ነው፡፡ እንጅ አውቀህ አይደለም፡፡ አሁን ያወጣኸውን ገንዘብ መልሰህ ወደ ኪስህ አስገባ እኔ አልቀበልም አሉ አቶ ላንቻ፡፡
አቶ ላንቻ ከድሬደዋ አዳማ እየተመላለሱ የሚነግዱ የታወቁ ቱጃር አልባሳ ነጋዴ ናቸው፡፡ ጨዋታቸው እየሞቀ ሄደ፡፡ አቶ ላንቻ ከተደገፉበት ወንበር ቀና አሉ፡፡
"ስምህን ማን አልከኝ"? አሉት፡፡ መጀመሪያ ነግሯቸው በጭዋታ የተነሳ ዘንግተውት ይሁን ተመስሎባቸው ደግመው መጠየቃቸው፡፡
"ያሬድ እባላለሁ አለ፡፡ ፊቱን ወደ አቶ ላንቻ መለስ አድርጎ፡፡
"አሁን ወዴት ነው የምትሄደው"? ፡፡
"ወደ ድሬ የምሄደው"፡፡
"እዛው ነዋሪ ነህ ወይስ ለስራ ነው የምትሄደው?፡፡
"አይ! ለስራ ነው፡፡ ነገ እመለሳለሁ፡፡ እቤት ከመቀመጥ ብዬ ትንሽ ሳልባጅ ቢጤ ጀምሬ ነበር፡፡ ሞልቶ ለማይሞላ ነገር ስንት ገዛኸው ዘጠኝ ፤ ስንት ሸጥከው ዘጠኝ ፤ ትርፉስ ምንድነው? ዘጥ ዘጥ እንደሚባለው የበሰለውን ከማጥፋት ውጭ ድካም ነው፡፡ ውጤት የለውም አላቸው፡፡ ንግግሩ የሚያስቅ ስለነበር ፈገግ አደረጋቸው፡፡
አቶ ላንቻ አለመተዋወቅ እንጅ አልባሳት ከሆነ የምትነግደው እኔ አዳማ ድረስ አመጣልህ ነበር አሉ፡፡
"አልባሳት ይነግዳሉ እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"አዎ፤ ነጋዴ ነኝ፡፡ አሁንም አራግፌ እየተመለስኩ ነው፡፡
"ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ እንዴው የሰው መተዋወቂያው መንገዱ ብዙ ነው አለ ያሬድ፡፡ ያገናኛቸው አጋጣሚ እያስገረመው፡፡
"ድሬ ደንበኛ አለህ የምትረከብበት"? ፡፡
"ደንበኛ እንኳን የለኝም፡፡ የጀመርኩት ቅርብ ጊዜ ስለሆነ ደንበኛ አላበጀሁም፡፡ ከአሸዋ ሜዳ ነው የምገዛው ፡፡
የዛሬ መገናኘታችን ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ አሁን እየደረስን ስለሆነ መነሃርያ ሳንገባ ወርደን አረፍ ብለን እንነጋገራለን" አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
ከመኪና ወርደው ወደ አንድ ሪስቶራንት አመሩ፡፡ አረፍ ብለው የሚጠጣ ለስላሳ አዘዙ፡፡ በመኪና ላይ የጀመሩትን ጭውውታቸውን እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
"አዳማ ውስጥ የራስዎ ቡቲክ አሎት እንዴ? አለ ያሬድ፡፡
"የራሴ እንኳን ቡቲክ የለኝም፡፡ አዳማ መነሃሪያ አካባቢ ቢያድግልኝ የሚባል የጅምላ አከፋፋይ ሱቅ አጠገብ የተከራየሁት ቡቲክ አለኝ፡፡ እዛ ነው የምሸጠው፡፡ ቦታውን ነገ አብረን ስንሄድ አሳይሃለሁ፡፡ አሁን እንሂድና እዚህ ድሬ ውስጥ ያለኝን ቡቲክ ላሳይህ፡፡ የሚያስፈልግህንም ገዝተህ እኔ በምጭንበት መኪና ጭነህ ነገ አብረን አንሄዳለን፡፡
ያሬድ ያገናኘውን አጋጣሚ እየመረቀ እንዴው ምን ዓይነት ደግ ሰው ነው፡፡ ያጋጠመኝ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ እያለ "አይደህና ነው፡፡ ለእኔም እዚህ ድረስ ከምለፋ ጥሩና መልካም ነው፡፡ እንዴው ውለታዎን ለመክፈል ያብቃኝ" አለ፡፡ ቀለስለስ እያለ፡፡
"አይ! ምንም ማለት አይደለም፡፡ የራሴም ስራ ነው፡፡ አሁን ከአንተ የምጠብቀው ታማኝ ሆኖ መገኘት ብቻ ነው"፡፡ ብለውት ሊያሳድሩት ወደ ቤታቸው ወሰዱት፡፡
በነጋታው በጥዋት ተነሱ፡፡ በተነጋገሩት መሰረት የሚያስፈልገውን ልብሶች ገዝቶ አብረው ወደ አዳማ ተጓዙ፡፡
👍64❤10😁1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እድላዊት
"የባሰ አለና አገርህን አትልቅ" እንደሚባለው እድላዊት ከወ/ ሮ በሰልፏ ሞት ጋር የተቃጠረች ይመስላል፡፡
ሳይሞቱ ቀድሜ ልውጣ ማለቷ በአካል ባትነሳም በመንፈስ ተነስታ ጉዞዋን ማሰቧ ፤ አፈር ሳታለብሽኝ ፤ ጥለሽኝ ልትሄጅ ነው? ያሏት፡፡ ወ/ሮ በሰልፏ ፤ ከህሊና የማይወጣ ጥያቄ አሳደረባት፡፡
እድላዊት ግን አፈር ሳታለብሳቸው አልሄደችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የስቃይና የመከራ ፅዋ ተቀብላ የወ/ሮ በሰልፏን ተስካር አወጣች፡፡ ሁሉን ነገር ምላድ ምላድ አሰያዘች፡፡ ልብሶቿን አጣጥባ ተነሳች፡፡
"አሁን ባዶሽን አትሄጅም"፡፡ ስንቅ አሰናድተሽ ነገ እሸኝሻለሁ ብሎ አስቀራት፡፡ እሸ ብላ ቀረች፡፡
ስንቅ ለማሰናዳት አልፈለገችም፡፡ ግን ደግሞ ፀበል አለመሔዷን እንዲነቃባት አትፈልግም፡፡ ትንሽ ዳቦ ቆሎ መሳይ አዘጋጀች፡፡ በነጋታው ጠዋት ከአቶ አርምዴ ጋር ተነሳች፡፡
አንዳንዴ እየተነጋገሩ ፤ አንዳንዴ የመለያየታቸው ነገር እያሳሰባቸው ፤ ለየብቻቸው ፣ በየራሳቸው ሃሳብ እየነጎዱ ሳይታወቃቸው ሸንኮራ ዮሐንስ ደረሱ፡፡
የሸንኮራ ዮሃንስ ፀበል ከመዲናችን አዲስ አበባ በ144 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 15/1654 ዓ/ም ገደማ ፀበሉ ለአባ ካሳ እንደተገለፀላቸው ይነገራል፡፡
ይህ ፀበል አይነ ስውር የሚያበራ ፤ ለምፅን የሚያነፃ ፤ ኤች አይቪን የሚፈውስ ፤ የአጥንት ካንሰርን ነቅሎ የሚጥል ፤ በአጠቃላይ ሰው ሰራሽ ይሁን ተፈጥሯዊ በሽታዎችን የሚፈውስ ለመሆኑ ብዙዎች ድነዋል፡፡ ተፈውሰዋል ፣ ምስክርነታቸውንም ተናግረዋል ፡፡
"የት አካባቢ ይሻልሻል"? አላት፡፡ ቤት ሊያሲዛት ፈልጎ ፤ አቶ አርምዴ፡፡
እድላዊት ሸንኮራን አልፋ ለመሄድ እንጅ ቤት ለመያዝ አልፈለገችም፡፡
"አሁን ቤት አልይዝም ወደ ፀበሉ ልሂድና ስመለስ እይዛለሁ፡፡አይታወቅም ወይም የማቀው ሰው ላገኝ እችላለሁ፡፡ ለእኔ ምንም አታስብ ፤ በቃ አንተም ተመለስ፡፡ ስራህን ትተህ ነው የመጣኸው፡፡ ላደርክልኝ ውለታና እገዛ እግዚአብሔር ሁሉንም እሱ ይክፈልልኝ አመሰግናለሁ" አለች፡፡ የሃዘን ስሜት በውስጧ እየተሰማት፡፡
አይ! እድል እኔ ምን አላደረግሁልሽም፡፡ ትንሽ ስንዴ ነገር ሸጥ እንኳን አድርጌ ፤ እንዳላዘጋጅልሽ ለመሄድ ቸኮልሽ፡፡
ለስምንት ዓመት አብራው የኖረችው የሟች እህቶቹ ምትክ እድላዊት ልትለየው በመወሰኗ ፤ የወንድ አንጀቱ እንደወላድ ተላወሰ፡፡ በአይኖቹ እንባው ግጥም አለበት፡፡
እድላዊት ከሞት አፋፍ ላይ ያተረፋትን አርምዴን መለየት አቃታት፡፡ ሆድ ባሳት፤ አለቀሰች፡፡ አርምዴ ያወራውን የሰማች አትመስልም፡፡
በፊቱ ላይ የወረደውን እንባ ጠራረገ፡፡ እድል ይበቃል አስካሁን ስታለቅሽ የኖርሽው፡፡ በትንሹም ፣ በትልቁም ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ የባሰ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ለማፅናናት ሞከረ፡፡
እዚህ ከቆየሽ ተመልሸ አይሻለሁ፡፡ ሰባት መቶ ብር ለአንድ ነገር ይሆንሻል ብሎ ሰጣት፡፡ እግዚአብሔር ከአንች ጋር ይሁን፡፡ ብሏት ተሰነባብተው አቋርጦት ወደ ነበረው ስራው ተመለሰ፡፡
ከተሰነባበቱ በኋላ፤ አቶ አርምዴ ከአካባቢው ዞር እስከሚልላት ድረስ ፀበልተኛ መሰለች፡፡ ከአካባቢው እስኪሰወር ጠብቃ ወደ ሸንኮራ ባልጭ የሚወስደውን የፈረስ ጋሪ ተሳፈረች፡፡
ሰው እያባረረ የሚከተላት መሰላት፡፡ ከፈረስ ጋሪ እንደወረደች ከባልጭ ሞጆ የሚያደርሳትን ያዘች፡፡
እድላዊት አሁንም መነሻዋን እንጅ መድረሻዋን አታውቅም፡፡ ሞጆ መነሃሪያ ደረሰች፡፡ ከተሳፈረችበት ባስ ወርዳ ልብስ የያዘችበትን ፌስታል አንጠልጥላ ስራ ፈላጊዎች ወደ ሚቀመጡበት አካባቢ አመራች፡፡
አዳማ ናዝሬት አዳማ ….እያለ ይለፈልፋል፡፡ ጆሯዋ ጥልቅ አለ፡፡ ሃሳቧን ሰርዛ አዳማ ናዝሬት የሚለውን ሚኒባስ ተሳፍራ ጉዞዋን ወደ አዳማ ናዝሬት አደረገች፡፡
እረዳቱ ውረዱ አለ፡፡ መነሃሪያ ደርሰው፡፡ እድላዊት ሞጆና አዳማ የሚራራቁ መስሏት ውረዱ ሲባል አላመነችም ነበር፡፡
ከሞጆ እስሯ ተቀምጦ የመጣ አንድ መልከ መልካም ፍሪዛም ወጣት ሲወርድ ለመጠየቅ እየፈራች አንተ አንተ…..ብላ ሳትጨርስ ሳይሰማት ጥሏት ወረደ፡፡
እድላዊት ያላት አማራጭ ወርዳ መጠየቅ ሆነ፡፡ ፌስታሏን አንጠልጥላ ወረደች፡፡
የአዳማ መነሃሪያ ደላሎች እንደተገለበጠ የንብ ቀፎ ከበቧት፡፡ እያዋከቡ አንዱ ደላላ የትነሽ ? ድሬ ከሆንሽ አንድ ሰው የቀረው ነው፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡ ያንጠለጠለችውን ፌስታል የመዝረፍ ያህል ነጥቋት ሄደ፡፡
ሁለተኛው ደላላ ደግሞ የት ነሽ ? አሰላ ከሆንሽ ባይሞላም አሁን ይወጣል፡፡ ነይ እያለ እጇን እየጎተተ ወደ አሰላ በሚሄደው አውቶቢስ ውስጥ አስገባት፡፡ የአውቶቢሱን በር ዘግቶባት ወረደ፡፡
እድላዊት ወዲያና ወዲህ ሲያዋክቧት ቀልቧ ተገፏል፡፡ አፏን በፕላስተር የታሸገች መስላለች፡፡ ይህ ሁሉ ትእሪት ሲካሄድ የምትሄድበትን አልተናገረችም ነበር፡፡
"አንች እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? ያልሞላ መኪና ውስጥ እቃሽ እኮ ተጭኗል፡፡ አሁን ልንወጣ ነው ነይ፡፡
የዘጋባትን በር ከፍቶ ይዟት ሄደ፡፡ ፌስታሏን ወስዶ የጫነባት ደላላ፡፡ እኔ ነኝ ፣ እኔ ነኝ የምጭነው፡፡ ግብግብ ተፈጠረ፡፡ ከአሰላው ደላላ ጋር፡፡
የድሬው አሸንፎ መኪናው ውስጥ ጎትቶ አስገባት፡፡ ገና መቀመጫ ሳይሰጣት የአውቶቢሱን በር ዘግቶ ተንቀሳቀሰ፡፡ እድላዊት እኔ አልሔድም ፣ እቃየን ስጠኝ፡፡ አውርደኝ ብትልም የሚሰማት አላገኘችም፡፡
"ሂጅ እዛጋ ክፍት ወንበር አለ፡፡ ተቀመጭ" አላት እረዳቱ፡፡
ግራ የገባት ከርታታዋ እድላዊት ተቀመጭ ከተባለችበት ወንበር ላይ ተቀመጠች፡፡ ከአንገቷ አቀርቅራ መኪናው ወንበር ላይ ተደገፈች፡፡ ለተሳፋሪ እንቅልፍ የወሰዳት መሰለች፡፡ የመውደቂያዋ ቦታ አሳስቧታል፡፡ ተጨንቃለች ፣ ሆዷ ተርፏ ተርፏ ይላል፡፡
አይኖቿ እንባ አቅረዋል፡፡ ምነው አምላኬ የት ልታደርሰኝ ነው?፡፡ መድረሻየን አላውቀውም፡፡
አንተን አምኘ ነው፡፡ እንግዴህ እንደፍቃድህ አድርገኝ እያለች ፈጣሪዋን እያለቀሰች ተማፀነችው፡፡
የራሳቸውን ሃሳብ እያወጡ እያወረዱ ስለስራ ያስባሉ፡፡ ከስሯ የተቀመጡት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ እድላዊት ለምን አቀርቅራ እንደምታለቅስ ግራ ገብቷቸዋል፡፡
"ምነው ልጄ ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው ? አሏት፡፡
"አይ! ምንም አልሆንኩም፡፡ አይኔን አሞኝ ነው አለች፡፡ ለራሷ ማልቀሷ ቢታወቃትም ፤ ስታለቅስ ግን ሰው የሰማት አልመሰላትም ነበር፡፡
"እና ማልቀሱ ጥሩ እኮ አይደለም፡፡ የባሰ ያምሻል አሉ፡፡ የእውነት አይኗን የታመመች መስሏቸው፡፡
ወ/ሮ ዘነቡ እድላዊትን በአለባበሷና በአነጋግሯ የገጠር ልጅ ለመሆኗ አልተጠራጠሩም ነበር፡፡
"እና አሁን የት ነው የምትሄጅው? አሏት ወ/ሮ ዘነቡ፡፡
እድላዊት የምትሄድበትን ቦታ አታውቅም፡፡ መጠጊያና ማረፊያ ለማግኘት ግን ሁሉንም አፍረጥርጣ መናገር የግድ ሆነባት፡፡
"የምሄድበትና መውደቂያዬን ባውቅማ ምን ያስለቅሰኝ ነበር፡፡ ያለማወቄ ነው እንጅ አለች፡፡ እንባዋ ሳያቋርጥ ግራና ቀኝ ጉልበቶቿ ላይ እየተንጠባጠበ፡፡
ከቤተሰቦቿ ጠፍታ መሆን አለበት ብለው ጠርጥረዋል ወ/ሮ ዘነቡ፡፡ ደግመው "ከየት ነው የመጣሽው? ታዲያ አሏት፡፡
"ከሸንኮራ ጅማ ነው የመጣሁት፡፡ ቤተሰቦቼን በህፃንነቴ ሞተውብኛል፡፡ ከዘመዶቼ ጋር አልስማማ ብዬ ጠፍቼ ነው፡፡
👍56❤9
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እጅግ በጣም ይቅርታ ስልኬ ስለጠፋ እረጅም ጊዜ ታሪኩን ሳለቅ ቀረሁ ወደኋላ መለስ ብለቹ ታሪኩን በማስታወስ ቀጥሉ እንደእግዚአብሔር ፍቃድ ከነገ ጀምሮ ሁለት ክፍል እለቃለሁ እንዲሁም ነገ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ እንጀምራለን የተከፋችሁብኝ አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ🙏
ያሬድ
ከገበያ መጥቶ ደክሞታል፡፡ ገና ሳይመሽ ከመኝታው ላይ ጋደም እንደማለት ብሏል፡፡
"ተመስገንን አብረን እንሄዳለን ብለኸው ነበር እንዴ"? አለች ፤ ባለቤቱ አበበች፡፡
"አዎ ፤ ብዬው ነበር፡፡ ገንዘብ እንዳዘጋጀ ነገረሽ እንዴ"?
"ትላንት አንተን ፈልጎ መጥቶ ነበር፡፡ ሳያገኝህ ሲቀር ለእኔ አጫውቶኛል፡፡ እንሂድ እስከምትለው ነው የሚጠብቀው" ፡፡
"ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ የመነገድ ፍላጎት ካለው አሁን ደግሞ ውሎ ገባ ስለሆነ የምንመጣው ቀን እንኳን ቢመሽም ሁለት መሆኑ አይከፋም፡፡ ከነገ ወዲያ ይዠው እሄዳለሁ"፡፡
ገና በደንብ አልነጋም፡፡ ያሬድም ከመኝታው አልተነሳም፡፡ አበበች አለ ፡፡ ሳይደጋግም በአንዴ የሚሰማ መስሎት፡፡ ነገር ግን የሚሰማው አላገኘም፡፡ አቤት የሚለው አጣ፡፡ ደግሞ ተጣራ፡፡ ያሬድ…..ያሬድ አለ፡፡ አቤት አለች አበበች፡፡ ብቅበይ አለ፡፡ በጥዋት ወደ ያሬድ ጋር የመጣው ተመስገን፡፡
ማነው በጥዋት ብቅበይ የሚለው ብላ ብቅ አለች፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች ? አለ" ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ተመስገን፡፡ አትገባም እንዴ ከብርድ ላይ ፡፡
"ይሁን አልገባም፡፡ ያሬድ የለም እንዴ ? ፡፡
"አለ ፤ ከመኝታውም አልተነሳም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም እንዴ ?
"ኧረ ደህናነኝ፡፡ ለዛ ላጫወትኩሽ ጉዳይ ነበር የመጣሁት ፡፡
"አይ! እሱንማ ከሆነ እኔም ማታ አጫውቸዋለሁ፡፡ ለመነገድ ፍላጎት ካለው ይዠው እሄዳለሁ ብሏል፡፡ ለማንኛውም ግባና አነጋግረው ፡፡
ተመስገን የመጣበትን ጉዳይ እንደተሳካለት አሰበ፡፡ ያሬድን ለማነጋገር ወደ ቤት ገባ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ? ፣ ደሞ ዛሬ በጥዋት አልተነሳህም፡፡ እንቅልፍ ነው ወይስ ድካም ነው?፡፡ ያስተኛህ ፡፡
"ሰላም አደርህ ተመስገን፡፡ ምን የትናንት ገበያ ውልቅልቅ አድርጎኛል፡፡ አሁን በደንብ ነግቷል ማለት ነው እንዴ? አለ፡፡ ከተኛበት መኝታ ተነስቶ እየተንጠራራ፡፡
"ስድስት ሰዓት ሆኖ ነግቷል ትላለህ እንዴ ፤ ለነገሩ ከተማ ለከተማ ስትመላለስ የከተማ ሰው ሆነሃል፡፡ እነኝህ ከተመኞች ሰዓት አስረው ቢይዙም ፤ የሚቆጥሩ መሆናቸውን እንጃ ፤ በየሰዓቱ ነው የሚበሉ
አለ፡፡ ተመስገን እንደማሾፍ ብሎ፡፡
"አይ! ተመስገን እነሱማ በሰዓት የማይበሉበት ጊዜ ስለሌላቸው ነው፡፡ ያለመቁጠር አይደለም፡፡ እንዲያውም እኛ ነን አንዴ ቁርስሠ ፣ አንዴ ምሳ ሰዓት ፣ ደረሰ እያልን ሰዓት የሚቃወመን ይመስል በቀን ሶስቴ ሳይበቃን አራተኛ መክሰስ እያልን የምንመገበው፡
"አይ! መልካም ነው" ብሎ "ለባለፈው ጉዳይ ነበር የመጣሁት" አለ ተመስገን ፡፡
"አበበች ማታ በጨዋታ አንስተን ነግራኛለች፡፡ እና ለመነገድ ፈልገሃል ማለት ነው?፡፡
"የመነገድ ፍላጎት እንኳን ብዙም የለኝም፡፡ እንዴው የዛችን የእህቴ ነገር አንጄቴ አልቆርጥ ብሎኝ ነው፡፡ መቼም እቤት ከመቀመጥ አካባቢንና አገርን ማወቅ አይከፋም፡፡ የእግዚአብሔር ስራም አይታወቅም፡፡ በዛውም እናገኛት ይሆናል"፡፡
"ጥሩ ነው ለማንኛውም ሃሳብህ አይከፋም፡፡ ነገ አብረን ማለድ ብለህ በጥዋት ና፡፡ ውሎ ገባ ስለምንመለስ እንዳይረፍድብን"፡፡
"እሽ በጥዋት እመጣለሁ፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
"በነጋታው በጥዋት ቡና ፈልቶ ተመስገን እየተጠበቀ ነው፡፡ ግን ቶሎ ሊመጣ አልቻለም፡፡ በቃ ቀርቶ ነው ብላ አበበች ቁርስ ልታቀርብ ስትል ተመስገን መጣ፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠው ተቀመጠ፡፡
"ምነው አረፈድህ" አለው ያሬድ
"ምን ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወሰደኝ አድሮ ሊነጋጋ አካባቢ ሸለብ አላደረገኝ መሰለህ ፡፡
"አይ! አንተ ሌሊቱን ሙሉ በሃሳብ ስትሄድ አድረህ ነዋ፡፡ ጥዋት በመነሻህ ሰዓት እንቅልፍ የጣለህ፡፡ በል አሁን የቡና ቁርሱን ያዝና ቡናውን ጠጥተን ቶሎ እንውጣ፡፡ የባልጪ መኪና ሳያመልጠን እንድረስበት፡፡ አንዴ ካመለጠን መመለስ ካልሆነ ሌላ መኪና አናገኝም፡፡
ባለቤቱን በይ እንግዴህ ከብት ሳይበዛ ከብቶቹን ውሃ አጠጫቸው ብሏት ተነስተው ከተመስገን ጋር ጉዞዋቸውን ወደ አዳማ ቀጠሉ፡፡
መኪና እንዳያመልጣቸው እየተጣደፉ ነው፡፡ ከመንገድ ላይ አንድ ጥቁር ሰው ከፊት ለፊታቸው ገጠማቸው፡፡
"ዛሬ ላይቀናን ነው መሰለኝ አለ ተመስገን፡፡ ውስጡ እንደመረበሽ እያለበት፡፡
"ምነው ምን አየህ አለው? ያሬድ፡፡
"ተመስገን የፍጥነት እርምጃውን ገታ አድርጎ ፤ መንገድ ስትሄድ አንድ ሰው ከገጠመህ የምትሄድበት አይቀናህም፡፡ አባቴ ሲናገር ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም እኛ አንድ ሰው ሰለገጠመን ብዬ ነው፡፡
ባያምንበትም ግን ሆዱ እንደመፍራት ብሏል፡፡ "ተው! እባክ ይህ የአንዳንድ ሰው አባባል ነው፡፡ አንተ ደግሞ ያባትህን አትከተል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ያድርገን እንግዴህ አለ፡፡ በፍራቻ ንግግርም ቢሆን፡፡
"እሱማ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው፡፡ እንዴው የሚባለውንና ነው እንጅ ያልኩህ፡፡
ያሬድ ነገሩን ተወት አድርጎ ፤ አሁን ቶሎ ቶሎ ራመድ ራመድ በል፡፡ ያ አቶ ላንቻ ብቻ ሳይቀድመን እንድንደርስበት፡፡
"የማነው አቶ ላንቻ? አለ ተመስገን፡፡
"ለእኔ ከድሬ አዳማ ድረስ አልባሳ የሚያመጡልኝ ናቸው፡፡ መቼም ብታያቸው የተባረኩ እና ደግ ሰው ናቸው፡፡
አሁንም ከሳቸው ተረክበን ነው፡፡ የምንመለሰው ከቀናን"፡፡
"እኔ እኮ ውሎ ገባ ስትመጣ በአየር መምጣት ጀመረ እንዴ ብየ ነበር፡፡ ለካስ አንተ አዳማ ድረስ የሚያመጣልህ ደንበኛ አግኝተህ ኖሯል፡፡እየከነፍህ የምትመጣው"፡፡
"መኪናው ሞልቶ አንድ ሰው ብቻ ቀርቶት ይጠባበቃል፡፡ እየተጣደፉ ደረሱ፡፡ ግን እረዳቱ ከአንድ ሰው ውጭ አልጭንም አላቸው፡፡ ጫነን አልጭንም ፤ ሲከራከሩ አንድ ረፍዶበት የነበር ሰው ረዳቱንም ሳይጠይቅ አልፎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ያሬድ ቢለምንም ፣ ቢማፀንም ሳያሳፍራቸው ጥሏቸው ሄደ፡፡
አላልኩህም፡፡ አንድ ሰው ጥሩ አይደለም ብየህ ነበር አለው ተመስገን፡፡
ጸያሬድ ተመስገን ያለውን የሰማው አይመስልም፡፡ ልቡ ያለው አቶ ላንቻ ጋር ነው፡፡ አንድ የጭነት መኪና ወደ አዳማ ልትወጣ ከመንገድ ላይ ቆማለች፡፡
"ይችን መኪና እንጠይቃት እስቲ ፤ ትጭነን እንደ ሆነ አለ ተመስገን፡፡
"እህል ጭና እያየሃት እንዴት እሽ ብለው ይጭኑናል፡፡ ያጠፋነው እኛ ነን፡፡ በጥዋት መምጣት ሲገባን አርፍደን፡፡ አሁን ያለን አማራጭ ወደ ቤት መመለስ ነው፡፡ ነገ ተመልሰን እንመጣለን፡፡ እንደው
የሚያነድደኝ እምነት ማጉደሌ ነው፡፡ መቼም መኪና አጥቶ ቀረ አይሉኝም፡፡ ሆነ ብሎ ነው እንጅ የሚሉኝ፡፡ እህል ወደ ጫነችው አይሱዚ ተጠጉ፡፡
ፈራ ተባ እያለ ማነህ ወንድም ወደ አዳማ እንደሆነ የምትሄደው መኪና ጥሎን ስለሄደ ነው፡፡ እባክህ ተባበረን ብሎ ሹፌሩን ጠየቀው ያሬድ፡፡
የመኪናው ሹፌር አላመነታም፡፡ "ስንት ናችሁ"? አለ፡፡
"ሁለት ነን አለ፤ ያሬድ፡፡
"ሁለት ሰው ከሆነ አልጭንም"፡፡ አንድ ሰው ከሆነ ጋቢና ግባ አለ፡፡ ባጭር ቃል ሹፌሩ፡፡
"እባክህን ወንድም ተባበረን ስለማንነጣጠል ነው፡፡ የምንሔደውም የታመመ ሰው ለማምጣት ነው፡፡
እንደምንም ተቸገርልን፡፡ ከላይም ቢሆን ተጭነን እንሄዳለን እያለ ሹፌሩን ተማፀነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
እጅግ በጣም ይቅርታ ስልኬ ስለጠፋ እረጅም ጊዜ ታሪኩን ሳለቅ ቀረሁ ወደኋላ መለስ ብለቹ ታሪኩን በማስታወስ ቀጥሉ እንደእግዚአብሔር ፍቃድ ከነገ ጀምሮ ሁለት ክፍል እለቃለሁ እንዲሁም ነገ ማታ ሁለት ሰአት ላይ ሌላ አዲስ ታሪክ እንጀምራለን የተከፋችሁብኝ አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ🙏
ያሬድ
ከገበያ መጥቶ ደክሞታል፡፡ ገና ሳይመሽ ከመኝታው ላይ ጋደም እንደማለት ብሏል፡፡
"ተመስገንን አብረን እንሄዳለን ብለኸው ነበር እንዴ"? አለች ፤ ባለቤቱ አበበች፡፡
"አዎ ፤ ብዬው ነበር፡፡ ገንዘብ እንዳዘጋጀ ነገረሽ እንዴ"?
"ትላንት አንተን ፈልጎ መጥቶ ነበር፡፡ ሳያገኝህ ሲቀር ለእኔ አጫውቶኛል፡፡ እንሂድ እስከምትለው ነው የሚጠብቀው" ፡፡
"ታዲያ ምን ችግር አለ፡፡ የመነገድ ፍላጎት ካለው አሁን ደግሞ ውሎ ገባ ስለሆነ የምንመጣው ቀን እንኳን ቢመሽም ሁለት መሆኑ አይከፋም፡፡ ከነገ ወዲያ ይዠው እሄዳለሁ"፡፡
ገና በደንብ አልነጋም፡፡ ያሬድም ከመኝታው አልተነሳም፡፡ አበበች አለ ፡፡ ሳይደጋግም በአንዴ የሚሰማ መስሎት፡፡ ነገር ግን የሚሰማው አላገኘም፡፡ አቤት የሚለው አጣ፡፡ ደግሞ ተጣራ፡፡ ያሬድ…..ያሬድ አለ፡፡ አቤት አለች አበበች፡፡ ብቅበይ አለ፡፡ በጥዋት ወደ ያሬድ ጋር የመጣው ተመስገን፡፡
ማነው በጥዋት ብቅበይ የሚለው ብላ ብቅ አለች፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች ? አለ" ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርህ ተመስገን፡፡ አትገባም እንዴ ከብርድ ላይ ፡፡
"ይሁን አልገባም፡፡ ያሬድ የለም እንዴ ? ፡፡
"አለ ፤ ከመኝታውም አልተነሳም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም እንዴ ?
"ኧረ ደህናነኝ፡፡ ለዛ ላጫወትኩሽ ጉዳይ ነበር የመጣሁት ፡፡
"አይ! እሱንማ ከሆነ እኔም ማታ አጫውቸዋለሁ፡፡ ለመነገድ ፍላጎት ካለው ይዠው እሄዳለሁ ብሏል፡፡ ለማንኛውም ግባና አነጋግረው ፡፡
ተመስገን የመጣበትን ጉዳይ እንደተሳካለት አሰበ፡፡ ያሬድን ለማነጋገር ወደ ቤት ገባ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ? ፣ ደሞ ዛሬ በጥዋት አልተነሳህም፡፡ እንቅልፍ ነው ወይስ ድካም ነው?፡፡ ያስተኛህ ፡፡
"ሰላም አደርህ ተመስገን፡፡ ምን የትናንት ገበያ ውልቅልቅ አድርጎኛል፡፡ አሁን በደንብ ነግቷል ማለት ነው እንዴ? አለ፡፡ ከተኛበት መኝታ ተነስቶ እየተንጠራራ፡፡
"ስድስት ሰዓት ሆኖ ነግቷል ትላለህ እንዴ ፤ ለነገሩ ከተማ ለከተማ ስትመላለስ የከተማ ሰው ሆነሃል፡፡ እነኝህ ከተመኞች ሰዓት አስረው ቢይዙም ፤ የሚቆጥሩ መሆናቸውን እንጃ ፤ በየሰዓቱ ነው የሚበሉ
አለ፡፡ ተመስገን እንደማሾፍ ብሎ፡፡
"አይ! ተመስገን እነሱማ በሰዓት የማይበሉበት ጊዜ ስለሌላቸው ነው፡፡ ያለመቁጠር አይደለም፡፡ እንዲያውም እኛ ነን አንዴ ቁርስሠ ፣ አንዴ ምሳ ሰዓት ፣ ደረሰ እያልን ሰዓት የሚቃወመን ይመስል በቀን ሶስቴ ሳይበቃን አራተኛ መክሰስ እያልን የምንመገበው፡
"አይ! መልካም ነው" ብሎ "ለባለፈው ጉዳይ ነበር የመጣሁት" አለ ተመስገን ፡፡
"አበበች ማታ በጨዋታ አንስተን ነግራኛለች፡፡ እና ለመነገድ ፈልገሃል ማለት ነው?፡፡
"የመነገድ ፍላጎት እንኳን ብዙም የለኝም፡፡ እንዴው የዛችን የእህቴ ነገር አንጄቴ አልቆርጥ ብሎኝ ነው፡፡ መቼም እቤት ከመቀመጥ አካባቢንና አገርን ማወቅ አይከፋም፡፡ የእግዚአብሔር ስራም አይታወቅም፡፡ በዛውም እናገኛት ይሆናል"፡፡
"ጥሩ ነው ለማንኛውም ሃሳብህ አይከፋም፡፡ ነገ አብረን ማለድ ብለህ በጥዋት ና፡፡ ውሎ ገባ ስለምንመለስ እንዳይረፍድብን"፡፡
"እሽ በጥዋት እመጣለሁ፡፡ ብሎት ተሰነባብተው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
"በነጋታው በጥዋት ቡና ፈልቶ ተመስገን እየተጠበቀ ነው፡፡ ግን ቶሎ ሊመጣ አልቻለም፡፡ በቃ ቀርቶ ነው ብላ አበበች ቁርስ ልታቀርብ ስትል ተመስገን መጣ፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠው ተቀመጠ፡፡
"ምነው አረፈድህ" አለው ያሬድ
"ምን ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወሰደኝ አድሮ ሊነጋጋ አካባቢ ሸለብ አላደረገኝ መሰለህ ፡፡
"አይ! አንተ ሌሊቱን ሙሉ በሃሳብ ስትሄድ አድረህ ነዋ፡፡ ጥዋት በመነሻህ ሰዓት እንቅልፍ የጣለህ፡፡ በል አሁን የቡና ቁርሱን ያዝና ቡናውን ጠጥተን ቶሎ እንውጣ፡፡ የባልጪ መኪና ሳያመልጠን እንድረስበት፡፡ አንዴ ካመለጠን መመለስ ካልሆነ ሌላ መኪና አናገኝም፡፡
ባለቤቱን በይ እንግዴህ ከብት ሳይበዛ ከብቶቹን ውሃ አጠጫቸው ብሏት ተነስተው ከተመስገን ጋር ጉዞዋቸውን ወደ አዳማ ቀጠሉ፡፡
መኪና እንዳያመልጣቸው እየተጣደፉ ነው፡፡ ከመንገድ ላይ አንድ ጥቁር ሰው ከፊት ለፊታቸው ገጠማቸው፡፡
"ዛሬ ላይቀናን ነው መሰለኝ አለ ተመስገን፡፡ ውስጡ እንደመረበሽ እያለበት፡፡
"ምነው ምን አየህ አለው? ያሬድ፡፡
"ተመስገን የፍጥነት እርምጃውን ገታ አድርጎ ፤ መንገድ ስትሄድ አንድ ሰው ከገጠመህ የምትሄድበት አይቀናህም፡፡ አባቴ ሲናገር ሰምቻለሁ፡፡ አሁንም እኛ አንድ ሰው ሰለገጠመን ብዬ ነው፡፡
ባያምንበትም ግን ሆዱ እንደመፍራት ብሏል፡፡ "ተው! እባክ ይህ የአንዳንድ ሰው አባባል ነው፡፡ አንተ ደግሞ ያባትህን አትከተል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ያድርገን እንግዴህ አለ፡፡ በፍራቻ ንግግርም ቢሆን፡፡
"እሱማ እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው፡፡ እንዴው የሚባለውንና ነው እንጅ ያልኩህ፡፡
ያሬድ ነገሩን ተወት አድርጎ ፤ አሁን ቶሎ ቶሎ ራመድ ራመድ በል፡፡ ያ አቶ ላንቻ ብቻ ሳይቀድመን እንድንደርስበት፡፡
"የማነው አቶ ላንቻ? አለ ተመስገን፡፡
"ለእኔ ከድሬ አዳማ ድረስ አልባሳ የሚያመጡልኝ ናቸው፡፡ መቼም ብታያቸው የተባረኩ እና ደግ ሰው ናቸው፡፡
አሁንም ከሳቸው ተረክበን ነው፡፡ የምንመለሰው ከቀናን"፡፡
"እኔ እኮ ውሎ ገባ ስትመጣ በአየር መምጣት ጀመረ እንዴ ብየ ነበር፡፡ ለካስ አንተ አዳማ ድረስ የሚያመጣልህ ደንበኛ አግኝተህ ኖሯል፡፡እየከነፍህ የምትመጣው"፡፡
"መኪናው ሞልቶ አንድ ሰው ብቻ ቀርቶት ይጠባበቃል፡፡ እየተጣደፉ ደረሱ፡፡ ግን እረዳቱ ከአንድ ሰው ውጭ አልጭንም አላቸው፡፡ ጫነን አልጭንም ፤ ሲከራከሩ አንድ ረፍዶበት የነበር ሰው ረዳቱንም ሳይጠይቅ አልፎ መኪናው ውስጥ ገባ፡፡ ያሬድ ቢለምንም ፣ ቢማፀንም ሳያሳፍራቸው ጥሏቸው ሄደ፡፡
አላልኩህም፡፡ አንድ ሰው ጥሩ አይደለም ብየህ ነበር አለው ተመስገን፡፡
ጸያሬድ ተመስገን ያለውን የሰማው አይመስልም፡፡ ልቡ ያለው አቶ ላንቻ ጋር ነው፡፡ አንድ የጭነት መኪና ወደ አዳማ ልትወጣ ከመንገድ ላይ ቆማለች፡፡
"ይችን መኪና እንጠይቃት እስቲ ፤ ትጭነን እንደ ሆነ አለ ተመስገን፡፡
"እህል ጭና እያየሃት እንዴት እሽ ብለው ይጭኑናል፡፡ ያጠፋነው እኛ ነን፡፡ በጥዋት መምጣት ሲገባን አርፍደን፡፡ አሁን ያለን አማራጭ ወደ ቤት መመለስ ነው፡፡ ነገ ተመልሰን እንመጣለን፡፡ እንደው
የሚያነድደኝ እምነት ማጉደሌ ነው፡፡ መቼም መኪና አጥቶ ቀረ አይሉኝም፡፡ ሆነ ብሎ ነው እንጅ የሚሉኝ፡፡ እህል ወደ ጫነችው አይሱዚ ተጠጉ፡፡
ፈራ ተባ እያለ ማነህ ወንድም ወደ አዳማ እንደሆነ የምትሄደው መኪና ጥሎን ስለሄደ ነው፡፡ እባክህ ተባበረን ብሎ ሹፌሩን ጠየቀው ያሬድ፡፡
የመኪናው ሹፌር አላመነታም፡፡ "ስንት ናችሁ"? አለ፡፡
"ሁለት ነን አለ፤ ያሬድ፡፡
"ሁለት ሰው ከሆነ አልጭንም"፡፡ አንድ ሰው ከሆነ ጋቢና ግባ አለ፡፡ ባጭር ቃል ሹፌሩ፡፡
"እባክህን ወንድም ተባበረን ስለማንነጣጠል ነው፡፡ የምንሔደውም የታመመ ሰው ለማምጣት ነው፡፡
እንደምንም ተቸገርልን፡፡ ከላይም ቢሆን ተጭነን እንሄዳለን እያለ ሹፌሩን ተማፀነው፡፡
👍85❤8👎2🥰1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቀነ ጎደሎ
ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ተነሱ፡፡ ወደ አዳማ ለመሄድ ተቻኩለዋል፡፡ ከቡቲካቸው አልባሳት እና ሌሎች እቃዎችንም ጫኑ፡፡ እንዳይረፍድባቸው ሹፌሩን ፍጥነት ጨምሮ እንዲነዳ አዘዙት፡፡ ከወትሮው በተለየ መልኩ ደብሯቸዋል፡፡ ሰውነታቸውን ከብዷቸዋል፡፡ ፊታቸውን ጨፍጓቸዋል፡፡ አፋቸውን እሬት እሬት ብሏቸዋል፡፡ ደጋግመው አፋቸውን በባዶው አላመጡት፡፡ ለውጥ ግን አላመጣላቸውም
ለሹፌሩ "ዛሬ ደግሞ ምን እንደሆንኩ እንጃ አፌን እሬት እሬት እያለኝ ነው" አሉት፡፡
"ምነው ቁርስ አልበሉም እንዴ?" ደግሞ ደስተኛ አይመስሉም፡፡ ደህና አይደሉም"? አለ፡፡ ሹፌራቸው ሰለሞን፡፡
"ኧረ ! ደህናነኝ፡፡ ብቻ ውስጤ እርብሽብሽ ብሏል፡፡ ሌሊትም ደግሞ ሲያቃዥኝ ነው ያደረው፡፡ ጥዋትም ቁርስ ወደ አፌ ስል አልዋጥ አለኝ፡፡ ምን እንደሆንኩ ለራሴም ሊገባኝ አልቻለም አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አስበውት ያላሳኩት ነገር አለ እንዴ"?
"አስቤ ያላሳካሁት ነገር እንኳን ያለ አይመስለኝም፡፡ ምንአልባት ዛሬ ማርፈዴ ብቻ ነው ትንሽ ያበሳጨኝ፡፡ ለምን እንደረፈደብኝም ሳላውቅ ከሩቅ የሚመጣ ደንበኛ ነበረኝ ያሬድ የሚባል፡፡ እንዴው ጠብቆኝ ሲያጣኝ ባልተመለሰ ብቻ እንጅ ቢያድግልኝ እንኳን ከሱቅ የትም ስለማይሄድ አምሽተንም ብንደርስ እናገኘዋለን፡፡ ለማንኛውም ነዳጅ ሰጠት አድርገህ ቶሎ ቶሎ ንዳው ፡፡
"እሽ አሁንም እኮ ፈጥነናል፡፡ ግን እኔም እኮ እጄ ሁሉ ተሳሰረብኝ" አለ ሰለሞን፡፡
ዘ
"ምነው አንተ ደግሞ ምን ሆነህ ነው ? ስትጨፍር እና ስትጠጣ አድረህ ፤ ምን አልባት እንቅልፍ መጥቶብህ እንዳይሆን"?
"እንኳን ስጠጣ ፣ ስጨፍር ላድር ፤ የጨብስም አጥቼ የዘጠኝ ብር አህያ መስየ ነው፡፡ ያደርኩት ፡፡
.አቶ ላንቻ የሰለሞን ፈሊጣዊ ንግግር አሳቃቸው፡፡ የዘጠኝ ብር አህያ ማለት ደግሞ ምን ማለት ነው? መቼም የዛሬ ልጆች የማታመጡት ጉድ የለም ፡፡
በመስኮት አይናቸውን ወርወር አደረጉ፡፡ ከበስተቀኝ በኩል የጋኔል ቁራጭ የሚመስል ጥቁር ውሻ ሊያቋርጣቸው ይሮጣል፡፡ ሰለሞን አፍጥነው ፣ አፍጥነው መኪናውን ፤ ይሔ ውሻ ሳያቋርጠን ፤ እንቅደመው አሉ፡፡ ሆዳቸው ተርፏ ተርፏ እያለ፡፡
ማርሽ ቀየረም ፤ ነዳጅ እረገጠም ፤ ውሻውን ግን ሊቀድመው አልቻለም፡፡ ውሻው አቋርጧቸው አለፈ፡፡
"ጭራሽ መንዳትም አቃተህ ፤ ውሻ መቅደም ያቅትህ አሉ፡፡ በፊታቸው ላይ የደም ስራቸው በንዴት እየተወጣጠረ፡፡
"መኪናው ሰርቪስ ከገባ ቆይቷል፡፡ ፍጥነት ጨምሬ ስነዳ እንዳይቆም ስለፈራሁ ነው፡፡ እንጅ ውሻ መቅደም አቅቶኝ አይደለም" ፡፡
የባሰ በጭንቀት ላይ ጭንቀት ሆነባቸው፡፡ መኪናው ከመንገድ ላይ እንዳይቆም ስጋቻ አደረባቸው፡፡ብቻ እንዳያዋርደን የባሰ ለማርፈዱ ሲቆጨን ከመንገድ ላይ ቆሞ፡፡ "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደ ሚባለው ከሁለት አጉል እንዳንሆን፡፡ እያሉ ከአፋቸው ተናግረው ሳይጨርሱ መኪናው ማዞሪያ ላይ መሪው አልዞር አለ፡፡ መስመር ሳተ፡፡ ሰለሞን ላብ በላብ ሆነ፡፡ ጎትቶ የማስገባት ያህል መልሶ ወደ መስመር አሰገባው፡፡
አቶ ላንቻ ከአሁን አሁን ተገለበጠ እያሉ ሰለሞን መሪው ሲያዞር ያገዙት ይመስል አንገታቸውን አብረው ያዞሩ ነበር፡፡
ከመስመር ሲገባ ትንሽ ትንፏሻቸው መለስ አለ፡፡ በል አሁን ቀስ ብለህ ንዳ የትም ጫካ እንዳታስቀረኝ አሉ ፤ እየፈሩም ቢሆን፡፡
"አሁን እግዚአብሔር ነው ያተረፈን ፡፡ ተገልብጦብኝ ነበር፡፡ እንጃ ብቻ ዛሬ በሰላም የምንገባ አልመስለኝም፡፡ ሆዴ ሁሉ በጣም ፈርቷል ፡፡
በስ መዓብ በል፡፡ ደግሞ ታሟርታለህ እንዴ ? አንዳንዴ ማሟረት ጥሩ አደለም፡፡ አፍ ሊከተል ይችላል አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አሁን ደግሞ ጭሱ መሽተት ጀምሯል፡፡
"እስኪ አቁመህ ውረድና እየው፡፡ የጭስ መውጫው ታፍኖ ይሆናል፡፡
ሰለሞን ወርዶ አየው፡፡ መኪናው ከመሽተት ውጭ የሚታይ ነገር አላገኘም፡፡ ተመልሶ ከሁለተኛ ማርሽ ወደ ሶስተኛ ማርሽ ቀይሮ ነዳ፡፡
የባሰ የመኪናው ድምፅ ተቀይሮ የመኪና ድምፅ መሆኑ ቀርቶ እንደ ወፍጮ መንኮራኮር ጀመረ፡፡ በስጋቻ አይኖቹ ተርገበገቡ፡፡ ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረበት፡፡ አንዳንዴ የመኪና መብራት ያበራል፡፡
የመኪና መብራት የምታበራው መንገዱ አልታይ አለህ"? እንዴ አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
አንዳንዴ ጨለማ እየመሰለኝ ነው እኮ፡፡ አሁንማ እጄ ሁሉ እየተንቀጠቀጠብኝ ነው፡፡ እስኪ ከእኔ ይሻሉ እንደሆን ይሞክሩት ፡፡
"እኔ ከአንተ እሻላለሁ ብለህ ነው፡፡ ምን አይነት ቀነ ጎደሎ ነው ፤ የገጠመን ዛሬ፡፡ እያሉ የሰለሞን ቦታ ቀይረው መኪናውን ለመንዳት መሪውን ጨበጡ፡፡ የባሰ እጃቸው ተሳሰረ፡፡ ግራና ቀኝ ዋዥቁ፡፡
"ፍሬን ይያዙ ፣ ፍሬን ይያዙ ፣ መስመር ስቷል፡፡ እያለ ጮኸ ሰለሞን፡፡ መኪናው ግን አልቆመም፡፡ እስከ አሁን ታግሸ አገለገልኳችሁ፡፡ የዚህ አለም ኑሮ ይበቃኛል፡፡ ብሎ አራት እግሩን ወደ ላይ ሰቅሎ ከመስመር በታች ወርዶ ተከረበተ፡፡
የፈሩት አልቀረም፡፡ ሰለሞን በደረሰው አደጋ ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ አቶ ላንቻ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸው ህይወታቸው ቢተርፍም ወደ ህክምና ሲሄዱ ጭንቅላታቸው በጣም ተጎድቶ ስለነበር ህክምናም ሳይደርሱ ህይወታቸው በመንገድ ላይ አለፈ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ ፕሮጀክት... 19 ቀን ብቻ ቀርቶታል ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ቀነ ጎደሎ
ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት ተነሱ፡፡ ወደ አዳማ ለመሄድ ተቻኩለዋል፡፡ ከቡቲካቸው አልባሳት እና ሌሎች እቃዎችንም ጫኑ፡፡ እንዳይረፍድባቸው ሹፌሩን ፍጥነት ጨምሮ እንዲነዳ አዘዙት፡፡ ከወትሮው በተለየ መልኩ ደብሯቸዋል፡፡ ሰውነታቸውን ከብዷቸዋል፡፡ ፊታቸውን ጨፍጓቸዋል፡፡ አፋቸውን እሬት እሬት ብሏቸዋል፡፡ ደጋግመው አፋቸውን በባዶው አላመጡት፡፡ ለውጥ ግን አላመጣላቸውም
ለሹፌሩ "ዛሬ ደግሞ ምን እንደሆንኩ እንጃ አፌን እሬት እሬት እያለኝ ነው" አሉት፡፡
"ምነው ቁርስ አልበሉም እንዴ?" ደግሞ ደስተኛ አይመስሉም፡፡ ደህና አይደሉም"? አለ፡፡ ሹፌራቸው ሰለሞን፡፡
"ኧረ ! ደህናነኝ፡፡ ብቻ ውስጤ እርብሽብሽ ብሏል፡፡ ሌሊትም ደግሞ ሲያቃዥኝ ነው ያደረው፡፡ ጥዋትም ቁርስ ወደ አፌ ስል አልዋጥ አለኝ፡፡ ምን እንደሆንኩ ለራሴም ሊገባኝ አልቻለም አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አስበውት ያላሳኩት ነገር አለ እንዴ"?
"አስቤ ያላሳካሁት ነገር እንኳን ያለ አይመስለኝም፡፡ ምንአልባት ዛሬ ማርፈዴ ብቻ ነው ትንሽ ያበሳጨኝ፡፡ ለምን እንደረፈደብኝም ሳላውቅ ከሩቅ የሚመጣ ደንበኛ ነበረኝ ያሬድ የሚባል፡፡ እንዴው ጠብቆኝ ሲያጣኝ ባልተመለሰ ብቻ እንጅ ቢያድግልኝ እንኳን ከሱቅ የትም ስለማይሄድ አምሽተንም ብንደርስ እናገኘዋለን፡፡ ለማንኛውም ነዳጅ ሰጠት አድርገህ ቶሎ ቶሎ ንዳው ፡፡
"እሽ አሁንም እኮ ፈጥነናል፡፡ ግን እኔም እኮ እጄ ሁሉ ተሳሰረብኝ" አለ ሰለሞን፡፡
ዘ
"ምነው አንተ ደግሞ ምን ሆነህ ነው ? ስትጨፍር እና ስትጠጣ አድረህ ፤ ምን አልባት እንቅልፍ መጥቶብህ እንዳይሆን"?
"እንኳን ስጠጣ ፣ ስጨፍር ላድር ፤ የጨብስም አጥቼ የዘጠኝ ብር አህያ መስየ ነው፡፡ ያደርኩት ፡፡
.አቶ ላንቻ የሰለሞን ፈሊጣዊ ንግግር አሳቃቸው፡፡ የዘጠኝ ብር አህያ ማለት ደግሞ ምን ማለት ነው? መቼም የዛሬ ልጆች የማታመጡት ጉድ የለም ፡፡
በመስኮት አይናቸውን ወርወር አደረጉ፡፡ ከበስተቀኝ በኩል የጋኔል ቁራጭ የሚመስል ጥቁር ውሻ ሊያቋርጣቸው ይሮጣል፡፡ ሰለሞን አፍጥነው ፣ አፍጥነው መኪናውን ፤ ይሔ ውሻ ሳያቋርጠን ፤ እንቅደመው አሉ፡፡ ሆዳቸው ተርፏ ተርፏ እያለ፡፡
ማርሽ ቀየረም ፤ ነዳጅ እረገጠም ፤ ውሻውን ግን ሊቀድመው አልቻለም፡፡ ውሻው አቋርጧቸው አለፈ፡፡
"ጭራሽ መንዳትም አቃተህ ፤ ውሻ መቅደም ያቅትህ አሉ፡፡ በፊታቸው ላይ የደም ስራቸው በንዴት እየተወጣጠረ፡፡
"መኪናው ሰርቪስ ከገባ ቆይቷል፡፡ ፍጥነት ጨምሬ ስነዳ እንዳይቆም ስለፈራሁ ነው፡፡ እንጅ ውሻ መቅደም አቅቶኝ አይደለም" ፡፡
የባሰ በጭንቀት ላይ ጭንቀት ሆነባቸው፡፡ መኪናው ከመንገድ ላይ እንዳይቆም ስጋቻ አደረባቸው፡፡ብቻ እንዳያዋርደን የባሰ ለማርፈዱ ሲቆጨን ከመንገድ ላይ ቆሞ፡፡ "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደ ሚባለው ከሁለት አጉል እንዳንሆን፡፡ እያሉ ከአፋቸው ተናግረው ሳይጨርሱ መኪናው ማዞሪያ ላይ መሪው አልዞር አለ፡፡ መስመር ሳተ፡፡ ሰለሞን ላብ በላብ ሆነ፡፡ ጎትቶ የማስገባት ያህል መልሶ ወደ መስመር አሰገባው፡፡
አቶ ላንቻ ከአሁን አሁን ተገለበጠ እያሉ ሰለሞን መሪው ሲያዞር ያገዙት ይመስል አንገታቸውን አብረው ያዞሩ ነበር፡፡
ከመስመር ሲገባ ትንሽ ትንፏሻቸው መለስ አለ፡፡ በል አሁን ቀስ ብለህ ንዳ የትም ጫካ እንዳታስቀረኝ አሉ ፤ እየፈሩም ቢሆን፡፡
"አሁን እግዚአብሔር ነው ያተረፈን ፡፡ ተገልብጦብኝ ነበር፡፡ እንጃ ብቻ ዛሬ በሰላም የምንገባ አልመስለኝም፡፡ ሆዴ ሁሉ በጣም ፈርቷል ፡፡
በስ መዓብ በል፡፡ ደግሞ ታሟርታለህ እንዴ ? አንዳንዴ ማሟረት ጥሩ አደለም፡፡ አፍ ሊከተል ይችላል አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
"አሁን ደግሞ ጭሱ መሽተት ጀምሯል፡፡
"እስኪ አቁመህ ውረድና እየው፡፡ የጭስ መውጫው ታፍኖ ይሆናል፡፡
ሰለሞን ወርዶ አየው፡፡ መኪናው ከመሽተት ውጭ የሚታይ ነገር አላገኘም፡፡ ተመልሶ ከሁለተኛ ማርሽ ወደ ሶስተኛ ማርሽ ቀይሮ ነዳ፡፡
የባሰ የመኪናው ድምፅ ተቀይሮ የመኪና ድምፅ መሆኑ ቀርቶ እንደ ወፍጮ መንኮራኮር ጀመረ፡፡ በስጋቻ አይኖቹ ተርገበገቡ፡፡ ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረበት፡፡ አንዳንዴ የመኪና መብራት ያበራል፡፡
የመኪና መብራት የምታበራው መንገዱ አልታይ አለህ"? እንዴ አሉ ፤ አቶ ላንቻ፡፡
አንዳንዴ ጨለማ እየመሰለኝ ነው እኮ፡፡ አሁንማ እጄ ሁሉ እየተንቀጠቀጠብኝ ነው፡፡ እስኪ ከእኔ ይሻሉ እንደሆን ይሞክሩት ፡፡
"እኔ ከአንተ እሻላለሁ ብለህ ነው፡፡ ምን አይነት ቀነ ጎደሎ ነው ፤ የገጠመን ዛሬ፡፡ እያሉ የሰለሞን ቦታ ቀይረው መኪናውን ለመንዳት መሪውን ጨበጡ፡፡ የባሰ እጃቸው ተሳሰረ፡፡ ግራና ቀኝ ዋዥቁ፡፡
"ፍሬን ይያዙ ፣ ፍሬን ይያዙ ፣ መስመር ስቷል፡፡ እያለ ጮኸ ሰለሞን፡፡ መኪናው ግን አልቆመም፡፡ እስከ አሁን ታግሸ አገለገልኳችሁ፡፡ የዚህ አለም ኑሮ ይበቃኛል፡፡ ብሎ አራት እግሩን ወደ ላይ ሰቅሎ ከመስመር በታች ወርዶ ተከረበተ፡፡
የፈሩት አልቀረም፡፡ ሰለሞን በደረሰው አደጋ ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ አቶ ላንቻ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸው ህይወታቸው ቢተርፍም ወደ ህክምና ሲሄዱ ጭንቅላታቸው በጣም ተጎድቶ ስለነበር ህክምናም ሳይደርሱ ህይወታቸው በመንገድ ላይ አለፈ፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ZOO አዲሱ ፕሮጀክት... 19 ቀን ብቻ ቀርቶታል ቢያንስ ገባ ብላችሁ እዩት አጭር ግዜ ነው የቀረው..ይመቻቹ
ለመጀመር 🦒👇
t.me/zoo_story_bot/game?startapp=ref405867113
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
👍63😢18❤3👎1
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አንድ አይጠጣም
የወጣት ሰውነቱ ፣ ለግላጋ ቁመናው ፣ ተቀያይሯል፡፡ ከአሁን በፊት ያልነበረውን ፂም አውጥቷል፡፡ ታዲያ በጉንጮቹ ላይ ግራና ቀኝ የወረደው አሪዝ መሳይ ፂሙ ጳጳስ አስመስሎታል፡፡ እንኳን ለማያቀው ለሚያውቀውም ሰው ተመስገንን መለየት ያስቸግር ነበር፡፡
ምግብ አዝዘው እየበሉ ነው፡፡ መብላቱን ተወት አድርጎ በሆቴሉ ዲም ላይት ይገረማል፡፡
"ከተሜ ማለት እንደ ዚህ ነው እንዴ"? አለ ተመስን፡፡
የተለየ ነገር አየህ"? አለው ያሬድ፡፡
"እኛም አገር ነጫጭ ሰው አስተናጋጅ ሆኖ ሳይ ነው"፡፡
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ………...ትገርማለህ የአገርህን ሰው እንኳን መለየት አቃተህ፡፡ እነዚህ እኮ የእኛ አገር ሰዎች ናቸው፡፡ ቅባት ስለተቀባቡ ነው፡፡ ነጭ የመሰሉህ ብሎት ለምግብ ማወራረጃ ቢራ ለማዘዝ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ዞር አደረገ፡፡ ከአንድ መልከ መልካም ህንዳዊ ከምትመስል ቆንጆ ሴት ልጅ ጋር አይኖቹ ተጋጨ፡፡
"ማነሽ እህት ቢራ ታዘዥን" አላት፡፡
"እኔ እኮ ቢራ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ያሰክረኛል ፣ አልጠጣም፡፡ ለራስህ እዘዝ ፤ ለእኔ ጠጅ የለመድሁት ይሻለኛል፡፡ አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አይ! ተመስገን ትገርማለህ ፤ እኔ እኮ ብዙ የምታቅ ትመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ምንም አታውቅም፡፡ ጠጅ እኮ እንደዚህ ያለ ሆቴል ውስጥ አይሸጥም፡፡ አለማወቅህ ነው እንጅ ከጠጁ ቢራው ነው የሚሻለው፡፡ ባይሆን አንድ ጠጥተህ ትተወዋለህ፡፡ ብሎት ቢራ እንዲጠጣ አሳመነው፡፡
"ምን አይነት ቢራ ልታዘዛችሁ አለች፡፡ የተጠራችው መልከ መልካም የህንድ ቆንጆ የምትመስል አስተናጋጅ፡፡
"በእናንተ አገር መጀመሪያ ሰላምታ አይፈቀድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"ኧረ ! ይባላል፡፡ እሽ ይቅርታ ብላ የእጅ ሰላምታ ሰጠቻቸው፡፡ ለዛ ያለው ፈገግታዋ በታከለበት፡፡
"ስምሽ ማን ይባላል"? አላት ያሬድ፡፡ እጁን ከእጇ ሳያላቅቅ፡፡
"የሽሃረግ እባላለሁ" ፡፡
"እሽ አመሰግናለሁ ብሏት የራሱን ስም ሳይነግራት ሁለት ሐረር ቢራ አምጭልን አላት፡፡
የሽሃረግ አስተናጋጅ አይደለችም፡፡ አስተናጋጅዋ ወደ ሱቅ ወታለች፡፡ እስከ ምትመለስ ግን ወደ ሆቴሉ የሚገቡትን ተስተናጋጆች ታስተናግዳለች፡፡
ታዲያ የሆቴሉ አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይና ሐምራዊ የተቀላቀለ በሚመስለው ዲም ላይት ውስጥ ሽር ሽር እያለች ስታስተናግድ አትኩሮ ለተመለከታት ፤ የቀሚስ አለባበሷ ፤ ኢትዮጵያዊነቷን ያለቀቀ ሆኖ በሰው እጅ የተሰራ ሳይሆን ከለግላጋ ሰውነቷ ጋር አምላክ አብሮ የፈጠረው ይመስል ነበር፡፡
ተመስገን የሽሃረግ እጁን ከጨበጠችው በኋላ፤ ከባንኮኒው ስትወጣና ስትገባ አብሯት በአይኖቹ ይመላለሳል፡፡
"ሊያመኝ ነው መሰለኝ"? ፡፡
"ጠጣበት ይለቅሃል፡፡ ዘና በል ደግሞ እንደ ልጅ አገረድ አትሽኮርመም"፡፡ "ምነው ደግሞ አይንህን በልጅቷ ላይ የምታንጃብበው"? አለው ያሬድ፡፡
"ኧረ ! አላንጃበብኩም፡፡ ግን ጓደኛዋ የወንድ ሱሪ ነው ያጠለቀችው፡፡ እሷ ደግሞ እንዴው ሳያት አለባበሷ አገረኛውን አለቀቀም፡፡ ታምራለች" ፡፡
"የቤት ልጅ ሆና ይሆናል፡፡ አለ ፤ ያሬድ፡፡
ያሬድ የአልባሳት ንግድ ከጀመረ ብቻ ሳይሆን በፊትም ከእናት አባቱ ቤት እያለ ስለከተማ ሴቶች አንዳንድ ነገሮችን ያውቃል፡፡ ለከተማ አዲስ አይደለም፡፡
ተመስገን አንድ ቢራ ያሰክረኛል ብሎ እየፈራ ቢጠጣውም አንድ ቢራ ግን አላሰከረውም፡፡ ለመድገም ፈልጓል፡፡
"ለካ ቢራ እንደዚህ ይጣፍጣል እንዴ"? አለ፡፡ ከጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን እየጨለጠ፡፡
ቢራ እንግዴህ አንድ አይጠጣም፡፡ ከሰከርክም ከአሁን በኋላ ፤ ስለማንቀሳቀስ መቼም መኝታችን ድረስ ገብተን መተኛት አያቅተንም፡፡ ብሎት ቢራ ሊደግሙ የሽሃረግን ጠራት፡፡
የሽሃረግ ደግሞ አስተናጋጇን መቅደስን ጠርታ እዛጋ እየጠሩሽ ነው፡፡ ታዘዣቸው አለች፡፡
መቅደስ "ቢራ ይደገም"? አለች፡፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"እሷ ብዙም አታስተናግድም፡፡ ሂሳብ ነው የምትቀበለው፡፡ የማስተናግደው እኔ ነኝ ፡፡
"እሽ ሁለት ሐረር ድገሚን" ፡፡
ተመስገን የጥላሁን ገሰሰ "ያቺ ቆንጆ ጥርሰ በረዶናት ፤ ውብ አይናማ ናት፡፡ የሚለውን ቀዝቀዝ ያለ ዜማ ልቡን ወሰድ አድርጎታል፡፡ አይኖቹን በየሽሃረግ ላይ ማንከራተቱን አላቋረጠም፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"አሁን ከቅድሙ ድብርቱ ለቀቅ አላደረገህም ?
ካለቀቀህ ቢራውን ደጋግምበት፡፡ አልያም ሐገረኛ ሙዚቃ አስከፍተን እንጨፍራለን" አለ ፤ ያሬድ፡፡ የያዘውን ቢራ ጎንጨት እያደረገ፡፡ አንዳንድ ቢራ አልበቃቸውም፡፡ አራት አራቱን ቆነደዱት፡፡ ተመስገን ሞቅ እያለው መጣ፡፡
ያሬድ አገረኛ ሙዚቃ የለም እንዴ? አለ ፤ ለመቅደስ፡፡
"ልቀይርላችሁ"? ፡፡
"አዎ፤ በዚያውም ቢራ ይዘሽልን ነይ" ፡፡
አገረኛው ሙዚቃ ተከፈተ፡፡ ተነስተው ግን አልጨፈሩም፡፡ በተቀመጡበት አንገታቸውን ያወዛውዛሉ፡፡ የጠጣው ሐረር ቢራ መንፈሱን ሰረቅ አድርጎታል፡፡"ያች ኮረዳ ዝምብላ ታየኛለች" አለ ተመስገን፡፡ የራሱ አትኩሮ ማየት ሳይታወቀው፡፡
"የቷ ኮረዳ"? ፡፡
"ያቺ እዛ ውስጥ ተቀምጣ አንገቷን ብቻ የምትታየው፡፡ ስሟ ማን ነበር ያለችው"?
"የሽሃረግን ነው የምትለው"?፡፡
"አዎ፤ ትክክል ነህ፡፡ ቅድም እኮ ስትጠራት ሰምቼ አሁን አፌ ላይ ጠፍቶብኝ ነው፡፡
"የፈለግሃት ትመስላለህ፡፡ ለማንኛውም የሽሃረግን ለማግኘት መቅደስን መጥራት አለብን፡፡ በእጁ አጨብጭቦ መቅደስን ጠራት፡፡
"ልድገማችሁ" ብላ ጠየቀች መቅደስ፡፡ ቢራ ፈልገው መስሏት፡፡
"ቢራ እንኳን አልጨረስንም፡፡ ለየሽሃረግ አንድ ቢራ
ስጫት" አለ ፤ ያሬድ፡፡
ቢራ ጠጥታ አታውቅም፡፡ ለስላሳ ከሆነ ነው እንጅ ፡፡
"እሽ ፤ ስጫት" ፡:
መቅደስ የታዘዘችውን ለስላሳ ከፊሪጅ አውጥታ ሰጠቻት፡፡
ማነው ያዘዘሽ ; አለቻት የሽሃረግ?፡፡
"እዛጋ የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ናቸው የጋበዙሽ፡፡ ብላ እነ ያሬድን በእጇ አመለከተቻት፡፡ ደግሞ ስምሽን ያውቁታል፡፡ ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ እንዴ?
"ኧረ ! ካለ ዛሬ አላየኋቸውም፡፡ ቅድም ነው ሱቅ ሄደሽ ሳስተናግዳቸው ስምሽ ማነው ሲሉኝ የነገርኳቸው" አለች፡፡ በዲም ላይቱ ፈገግታ ተመስገንን በስርቆት እየተመለከተች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አንድ አይጠጣም
የወጣት ሰውነቱ ፣ ለግላጋ ቁመናው ፣ ተቀያይሯል፡፡ ከአሁን በፊት ያልነበረውን ፂም አውጥቷል፡፡ ታዲያ በጉንጮቹ ላይ ግራና ቀኝ የወረደው አሪዝ መሳይ ፂሙ ጳጳስ አስመስሎታል፡፡ እንኳን ለማያቀው ለሚያውቀውም ሰው ተመስገንን መለየት ያስቸግር ነበር፡፡
ምግብ አዝዘው እየበሉ ነው፡፡ መብላቱን ተወት አድርጎ በሆቴሉ ዲም ላይት ይገረማል፡፡
"ከተሜ ማለት እንደ ዚህ ነው እንዴ"? አለ ተመስን፡፡
የተለየ ነገር አየህ"? አለው ያሬድ፡፡
"እኛም አገር ነጫጭ ሰው አስተናጋጅ ሆኖ ሳይ ነው"፡፡
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ………...ትገርማለህ የአገርህን ሰው እንኳን መለየት አቃተህ፡፡ እነዚህ እኮ የእኛ አገር ሰዎች ናቸው፡፡ ቅባት ስለተቀባቡ ነው፡፡ ነጭ የመሰሉህ ብሎት ለምግብ ማወራረጃ ቢራ ለማዘዝ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ዞር አደረገ፡፡ ከአንድ መልከ መልካም ህንዳዊ ከምትመስል ቆንጆ ሴት ልጅ ጋር አይኖቹ ተጋጨ፡፡
"ማነሽ እህት ቢራ ታዘዥን" አላት፡፡
"እኔ እኮ ቢራ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ያሰክረኛል ፣ አልጠጣም፡፡ ለራስህ እዘዝ ፤ ለእኔ ጠጅ የለመድሁት ይሻለኛል፡፡ አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አይ! ተመስገን ትገርማለህ ፤ እኔ እኮ ብዙ የምታቅ ትመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ምንም አታውቅም፡፡ ጠጅ እኮ እንደዚህ ያለ ሆቴል ውስጥ አይሸጥም፡፡ አለማወቅህ ነው እንጅ ከጠጁ ቢራው ነው የሚሻለው፡፡ ባይሆን አንድ ጠጥተህ ትተወዋለህ፡፡ ብሎት ቢራ እንዲጠጣ አሳመነው፡፡
"ምን አይነት ቢራ ልታዘዛችሁ አለች፡፡ የተጠራችው መልከ መልካም የህንድ ቆንጆ የምትመስል አስተናጋጅ፡፡
"በእናንተ አገር መጀመሪያ ሰላምታ አይፈቀድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"ኧረ ! ይባላል፡፡ እሽ ይቅርታ ብላ የእጅ ሰላምታ ሰጠቻቸው፡፡ ለዛ ያለው ፈገግታዋ በታከለበት፡፡
"ስምሽ ማን ይባላል"? አላት ያሬድ፡፡ እጁን ከእጇ ሳያላቅቅ፡፡
"የሽሃረግ እባላለሁ" ፡፡
"እሽ አመሰግናለሁ ብሏት የራሱን ስም ሳይነግራት ሁለት ሐረር ቢራ አምጭልን አላት፡፡
የሽሃረግ አስተናጋጅ አይደለችም፡፡ አስተናጋጅዋ ወደ ሱቅ ወታለች፡፡ እስከ ምትመለስ ግን ወደ ሆቴሉ የሚገቡትን ተስተናጋጆች ታስተናግዳለች፡፡
ታዲያ የሆቴሉ አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይና ሐምራዊ የተቀላቀለ በሚመስለው ዲም ላይት ውስጥ ሽር ሽር እያለች ስታስተናግድ አትኩሮ ለተመለከታት ፤ የቀሚስ አለባበሷ ፤ ኢትዮጵያዊነቷን ያለቀቀ ሆኖ በሰው እጅ የተሰራ ሳይሆን ከለግላጋ ሰውነቷ ጋር አምላክ አብሮ የፈጠረው ይመስል ነበር፡፡
ተመስገን የሽሃረግ እጁን ከጨበጠችው በኋላ፤ ከባንኮኒው ስትወጣና ስትገባ አብሯት በአይኖቹ ይመላለሳል፡፡
"ሊያመኝ ነው መሰለኝ"? ፡፡
"ጠጣበት ይለቅሃል፡፡ ዘና በል ደግሞ እንደ ልጅ አገረድ አትሽኮርመም"፡፡ "ምነው ደግሞ አይንህን በልጅቷ ላይ የምታንጃብበው"? አለው ያሬድ፡፡
"ኧረ ! አላንጃበብኩም፡፡ ግን ጓደኛዋ የወንድ ሱሪ ነው ያጠለቀችው፡፡ እሷ ደግሞ እንዴው ሳያት አለባበሷ አገረኛውን አለቀቀም፡፡ ታምራለች" ፡፡
"የቤት ልጅ ሆና ይሆናል፡፡ አለ ፤ ያሬድ፡፡
ያሬድ የአልባሳት ንግድ ከጀመረ ብቻ ሳይሆን በፊትም ከእናት አባቱ ቤት እያለ ስለከተማ ሴቶች አንዳንድ ነገሮችን ያውቃል፡፡ ለከተማ አዲስ አይደለም፡፡
ተመስገን አንድ ቢራ ያሰክረኛል ብሎ እየፈራ ቢጠጣውም አንድ ቢራ ግን አላሰከረውም፡፡ ለመድገም ፈልጓል፡፡
"ለካ ቢራ እንደዚህ ይጣፍጣል እንዴ"? አለ፡፡ ከጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን እየጨለጠ፡፡
ቢራ እንግዴህ አንድ አይጠጣም፡፡ ከሰከርክም ከአሁን በኋላ ፤ ስለማንቀሳቀስ መቼም መኝታችን ድረስ ገብተን መተኛት አያቅተንም፡፡ ብሎት ቢራ ሊደግሙ የሽሃረግን ጠራት፡፡
የሽሃረግ ደግሞ አስተናጋጇን መቅደስን ጠርታ እዛጋ እየጠሩሽ ነው፡፡ ታዘዣቸው አለች፡፡
መቅደስ "ቢራ ይደገም"? አለች፡፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"እሷ ብዙም አታስተናግድም፡፡ ሂሳብ ነው የምትቀበለው፡፡ የማስተናግደው እኔ ነኝ ፡፡
"እሽ ሁለት ሐረር ድገሚን" ፡፡
ተመስገን የጥላሁን ገሰሰ "ያቺ ቆንጆ ጥርሰ በረዶናት ፤ ውብ አይናማ ናት፡፡ የሚለውን ቀዝቀዝ ያለ ዜማ ልቡን ወሰድ አድርጎታል፡፡ አይኖቹን በየሽሃረግ ላይ ማንከራተቱን አላቋረጠም፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"አሁን ከቅድሙ ድብርቱ ለቀቅ አላደረገህም ?
ካለቀቀህ ቢራውን ደጋግምበት፡፡ አልያም ሐገረኛ ሙዚቃ አስከፍተን እንጨፍራለን" አለ ፤ ያሬድ፡፡ የያዘውን ቢራ ጎንጨት እያደረገ፡፡ አንዳንድ ቢራ አልበቃቸውም፡፡ አራት አራቱን ቆነደዱት፡፡ ተመስገን ሞቅ እያለው መጣ፡፡
ያሬድ አገረኛ ሙዚቃ የለም እንዴ? አለ ፤ ለመቅደስ፡፡
"ልቀይርላችሁ"? ፡፡
"አዎ፤ በዚያውም ቢራ ይዘሽልን ነይ" ፡፡
አገረኛው ሙዚቃ ተከፈተ፡፡ ተነስተው ግን አልጨፈሩም፡፡ በተቀመጡበት አንገታቸውን ያወዛውዛሉ፡፡ የጠጣው ሐረር ቢራ መንፈሱን ሰረቅ አድርጎታል፡፡"ያች ኮረዳ ዝምብላ ታየኛለች" አለ ተመስገን፡፡ የራሱ አትኩሮ ማየት ሳይታወቀው፡፡
"የቷ ኮረዳ"? ፡፡
"ያቺ እዛ ውስጥ ተቀምጣ አንገቷን ብቻ የምትታየው፡፡ ስሟ ማን ነበር ያለችው"?
"የሽሃረግን ነው የምትለው"?፡፡
"አዎ፤ ትክክል ነህ፡፡ ቅድም እኮ ስትጠራት ሰምቼ አሁን አፌ ላይ ጠፍቶብኝ ነው፡፡
"የፈለግሃት ትመስላለህ፡፡ ለማንኛውም የሽሃረግን ለማግኘት መቅደስን መጥራት አለብን፡፡ በእጁ አጨብጭቦ መቅደስን ጠራት፡፡
"ልድገማችሁ" ብላ ጠየቀች መቅደስ፡፡ ቢራ ፈልገው መስሏት፡፡
"ቢራ እንኳን አልጨረስንም፡፡ ለየሽሃረግ አንድ ቢራ
ስጫት" አለ ፤ ያሬድ፡፡
ቢራ ጠጥታ አታውቅም፡፡ ለስላሳ ከሆነ ነው እንጅ ፡፡
"እሽ ፤ ስጫት" ፡:
መቅደስ የታዘዘችውን ለስላሳ ከፊሪጅ አውጥታ ሰጠቻት፡፡
ማነው ያዘዘሽ ; አለቻት የሽሃረግ?፡፡
"እዛጋ የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ናቸው የጋበዙሽ፡፡ ብላ እነ ያሬድን በእጇ አመለከተቻት፡፡ ደግሞ ስምሽን ያውቁታል፡፡ ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ እንዴ?
"ኧረ ! ካለ ዛሬ አላየኋቸውም፡፡ ቅድም ነው ሱቅ ሄደሽ ሳስተናግዳቸው ስምሽ ማነው ሲሉኝ የነገርኳቸው" አለች፡፡ በዲም ላይቱ ፈገግታ ተመስገንን በስርቆት እየተመለከተች፡፡
👍47❤9
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
"አንች ጠጭ ጠጭ ምንም አይልሽም ብለሽኝ አሁን እኮ አዞረኝ" አለች፡፡ ለጓደኛዋ መቅደስ፡፡
"አንዱን ቢራ ጨረሽው እንዴ? ትገርሚያለሽ እንደለስላሳ ነው ስልሽ እንደለስላሳ ጨለጥሽው፡፡ በይ አሁን ቀስ ብለሽ አንድ ድገሚና ከዚያ በኋላ ይበቃሻል፡፡ ለነገሩ ቢራ አንድ ስለማይጠጣ ነው እንጅ በአንድ ቢበቃሽ ጥሩ ነበር፡፡
"አሁን አመመኝ እያልኩሽ ድገሚና ጠጭ ትይኛለሽ ? ብላ ብትኮሳተርም መድገሟ አልቀረም ሁለተኛ ቢራዋን አስከፈተች፡፡
በስካር መንፈስ ምሽቱ ወደ ቀን ተቀይሮበታል፡፡ አይመሽም እንዴ? ሆቴሉ አይዘጋም? ይላል ፤ ተመስን በውስጡ ፡፡
"ከአሁን በፊት ከሴት ጋር ተኝተህ ታውቃለህ"? እንዴ አለው ያሬድ፡፡
"ከሴት ጋር መተኛት አይደለም ለመተኛትም አውርቼ አላውቅም፡፡ ዛሬ ግን ብተኛ ምን እሆናለሁ፡፡
"እና የትኛዋ ትሻልሃለች"?፡፡
"የሽሃረግ ትሻለኛለች ፤ እሽ ካለች፡፡
"እሽ ፤ እንጠይቃታለን ግን እንደ ገጠር ሴት ዝም ብለው እሽ አይሉም፡፡ ገንዘብ ይጠይቃሉ፡፡
"ለብር ችግር የለም፡፡ ብቻ እሽ አሰኝልኝ ፡፡
ያሬድ መቅደስን ለብቻዋ ጠርቶ ለማነጋገር ፈልጓል፡፡ ከመቀመጫው ተነሳ፡፡ መቅደስን ጠራት፡፡ ከሰው ጋር እንዴ? ብሎ ጠየቃት፡፡
"እኔ ከሰው ጋር ነኝ፡፡ የሽሃረግ ደግሞ እንደዚ አይነት ስራ ሰርታ ስለማታቅ አትወጣም አለችው፡፡
ደግሞ የከተማ ሴት እንደ ገጠር ነው እንዴ? በገንዘብ እሽ አትልም? ፡፡
"እሱማ ልክ ነህ ፤ እሷ ግን ስለማትሰራ ነው፡፡
ጓደኛየ ከአሁን በፊት ከሴት ጋር ተኝቶ አያውቅም፡፡ ዛሬ ምን እንደነካው እንጃ በየሽሃረግ አብዷል አላት፡፡
ብቻ ከእሷ ለመስማት እሽ ካለች እጠይቃታለሁ፡፡ ብላ ልጠይቃት እየፈራች ቢሆንም ተጠጋቻት፡፡ የሽሃረግ የጠጣችው የሐረር ቢራ አስክሯታል፡፡ ወደ ኋላ ያሰረችውን ሐር የሚመስለውን ፀጉሯን ለቃዋለች፡፡
ታዲያ አይኗን ሸፍኖት ትንሽ ትንሽ ነበር ፊቷ የሚታየው፡፡
መቅደስ የጠጣችው ቢራ እሷንም ሞቅ አድርጓት ስለነበር የሽሃረግን ሳትፈራ ስሟን አቆላምጣ የሺዬ ያሰውዬ ፎንቅቄያለሁ እያለ ነው አለቻት፡፡
"የቱ ነው"? አለች፡፡ ፀጉሯን ከፊቷ ላይ ገለጥ እያደረገች፡፡
ቢራ ከጋበዙሽ አንደኛው ፡፡ ያ የፂሙ አሪዝ የሚያምረው ሰውዬ፡፡ ደግሞ ሴት የሚባል አውጥቶ አያውቅም፡፡ ቢራ እራሱ የተማከራችሁ ይመስል እንደ አንችው ዛሬ ነው ፤ የጀመረው አለቻት፡፡
"አንች በምን አወቅሽ ዛሬ ቢራ መጀመሩን ?፡፡
አብሮት ያለው ጓደኛው ነው የነገረኝ፡፡
"እኔ እንደዚህ አይነት ስራ እንደማልሰራ እያወቅሽ ፤ ለምን ትጠይቂኛለሽ"? አለች፡፡ ውስጧ ፍራት ፍራት እየተሰማት፡፡
እሱንማ አውቃለሁ፡፡ ግን አንች እስከመቼ ድረስ ነው? ወንድ የማትፈልጊው ፤ የጠየቀሽን ሁሉ አልፈልግም እያልሽ፡፡ ላይፍሽን በአሁን ሰዓት ካልተጠቀምሽበት መቼ ልትጠቀሚበት ነው?፡፡ ደግሞ ጊዜሽ ካለፈ ወዲያ ማንም ሊጠይቅሽ አይደለም ዞር ብሎ የሚያይሽ አታገኝም፡፡ ይልቁንም ዛሬ እትዬም ስለሌለች አብረሽው እደሪ አለቻት፡፡
እሳትን በእሳት እንደ ሚባለው ሴትን በሴት አሳምኖ በቁጥጥር ስር ማድረግ በሴቶች የተለመደ መሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡
ጊዜሽ ካለፈ ዞር ብሎ የሚያይሽ አታገኝም፡፡ ያለቻት ህሊናዋን በመርፌ የተወጋች ያህል ተሰማት፡፡ በትካዜ ተዋጠች፡፡ መጀመሪያም ልቧን በአይን አፋርነቱና በጉንጩ ላይ መስመር ሰርቶ በወረደው አሪዛም ፂሙ አሸፍቶ የወሰደባት ተመስገን እንኳን ለሴት ልጅ ለወንድ ልጅ ያማልል ነበር፡፡
"እትየ ስትመጣ ካልነገርሽብኝ እኔም ወድጀዋለሁ"፡፡ አለቻት የልብ ትርታዋ ከመጠን አልፎ ቁና ቁና እያስተነፈሳት፡፡
አልነግርብሽም፡፡ ደግሞ እኔ የምናግረው ጣቱን የሚጠባ ህፃን አደረግሽኝ እንዴ ብላት "በይ አሁን
ሰውም ስለሌለ እንዘጋጋና እኔም ሰው እየጠበቀኝ ነው እንተኛ አለቻት፡፡
"እምቢ ሳትል አትቀርም አለ ፤ ያሬድ፡፡
የከተማ ሴት ገንዘብ ነው የሚፈልጉት አላልከኝም" እንዴ አለ ፤ ተመስገን፡፡
የዚች የተለየ ነው እባክህ ብሎ ሌላም ደግሞ ሳይናገር መቅደስ ጠጡና ተነሱ ልንዘጋ ነው አለች፡፡
ተመስገን መሸ እንዴ? አለ፡፡
አልታወቀህም እንዴ? ከመምሸቱም ሊነጋ ተቃርቧል፡፡ እንዴውም የእኛ ብቻ ነው፡፡
ያልተዘጋው እንጅ የሁሉም ሆቴሎች ተዘግተዋል አለች ፤ መቅደስ፡፡
"እሽ ፤ እንነሳለን ግን የሽሃረግ ምን አለችሽ"? አለ
መቅደስ በስንት ልመና እሽ አስብያታለሁ፡፡ አሁንም እየፈራች ስለሆነ እናንተ ተነሱና አልጋ ቤት ጠብቁኝ፡፡ እኔ ይዣት እመጣለሁ አለች፡፡
ተንገዳገደ፡፡ ደግፎት ወደ መኝታ ቤት ገቡ፡፡
መቅደስ ሆቴሉን ዘጋግታ ከጨረሰች በኋላ፤ የሽሃረግን የሆቴሉ ዘበኛ እንዳያያት ወደ ሽንት ቤት የሚሄዱ አስመስላ ወደ እነ ያሬድ አልጋ ቤት አስገባቻት፡፡ ያሬድ ለሚተኛበት ሌላ አልጋ ከፍታለት አብሯት ወደ ሚያድረው ሰው ጋር ተመለሰች ፡፡
ለተመስገን ችግር የሚያጋጥምህ ከሆነ እዚህኛው አልጋ ቤት ነው የምተኛው፡፡ ነገ በጥዋት ወደ አቶ ላንቻ ቤት እንሄዳለን ብሎት ሁለተኛ ወደ ያዘው አልጋ ሄዶ ተኛ፡፡
የመኝታው በር ተዘጋ፡፡ ልብሳቸውን አወላለቁ፡፡ ከአሁን በፊት እንደሚተዋወቁ ፍቅረኛ ተቃቀፉ፡፡ ታምሪያለሽ ፤ አንተም ታምራለህ፡፡ ብቻ የሚል ቃል ተነጋግረው በለበሱት ብርድልብስ ውስጥ ከንፈር ለከንፈር ተፈላልገው ተገናኙ፡፡
የሁለቱም የሰውነት ሙቀት ጨመረ፡፡ ሳይታወቃቸው የተመስገን እግሮች በየሻረግ እግሮች ውስጥ ተጠላለፉ፡፡ በስካር መንፈስ ጉዳያቸውን ከፈፀሙ በኋላ ሁለቱም እራሳቸውን ሳቱ፡፡ መተቃቀፉና መሳሳሙ ቀረ፡፡ ድጋሜም አልተገናኙም፡፡ የለሊቱ ጨለማ ለቆ የቀኑ ብርሃን ተተካ፡፡
ያሬድ እሱም በስካር መንፈስ የመኝታ በሩን ከፍቶ እንደ ገባ ጫማውን እንኳን አላወለቀም፡፡ የወደቀበትን አያውቀም፡፡ ስካርና እንቅልፉን አሳልፎ ከተኛበት መኝታ ላይ ባነነ፡፡ ጫማውን ሳያወልቅ በመተኛቱ ተገረመ፡፡እንደዚህ እራሴን እስከምስት ድረስ ሰክሬ ኖሯል፡፡ ወይ ነዶ የሰውዬው ልጅ እያለ ተነሳ፡፡ በሩን ከፈተ፡፡ ሌሊቱ ነግቶ ቀን ቀን እየሸተተ ነው፡፡
የስካር ፊቱን ታጠበ፡፡ ልቡ አቶ ላንቻ ጋር ለመሄድ ተቻኩሏል፡፡ የአልጋው በር አልተዘጋም፡፡ ገርበብ ብሏል፡፡ ሳይዘጉት ይሆን እንዴ? የተኙት እያለ ገርበብ ያለውን በር ከፈት አድርጎ ገባ፡፡
የሽሃረግ ከተኛችበት ስትነሳ ከማታውቀው ሰው ጋር ተኝታ የንፅህና ክብሯን በመስጠቷ የሞት ያህል ተሰምቷታል፡፡ በሁለት እጆቿ እራሷን ደግፋ ከአንገቷ ወደ መሬት አቀርቅራ ከመኝታው ላይ ተቀምጣለች፡፡ የተፈጠረውንና ያደረገችውን ሁሉ ለማስታወስ እየሞከረች ከህሊናዋ ጋር እየተሟገተች ሳለ ያሬድ በር ከፍቶ ገባ፡፡ ካቀረቀረችበት ቀና አለች፡፡ ከያሬድ ጋር አይን ለአይን ተጋጩ፡፡ ያሬድ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡ ድንጋጤ ተሰማው፡፡
የሽሃረግን ደጋግሞ አትኩሮ ተመለከታት፡፡ ማታ በዲም ላይትና በፌር ቅባት ህንዳዊ መስላ የታየችው የፊት ላይ ቅባት ተወግዶ የኢትዮጵያዊነት ደም ግባቷ ተመልሷል፡፡ የጠይም ለግላጋ ቆንጆ መሆኗን በደንብ ይታያል፡፡ የሚያውቃት የሚያውቃት መሰለው፡፡
ተመስገን የት እንደ ሄደ እንኳን አልጠየቃትም፡፡ ወደ ተቀመጠችበት መኝታ ተጠጋ፡፡
ምነው? የማውቅሽ መሰለኝ፡፡ ግን ስምሽ ትክክለኛ የሽሃረግ ነው? አላት፡፡
የሽሃረግ ጭንቅላቷን በመጥረቢያ እንደተመታች ያህል ባለችበት ክው ብላ ቀረች፡፡ ያሬድን አፍጣ ፣ ደግማ ፣ ደጋግማ አየችው፡፡
"የየየየየየየየየየየየየ..ታ...ውቀኛለህ"? አለች፡፡ አፏ እየተንተባተበ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
"አንች ጠጭ ጠጭ ምንም አይልሽም ብለሽኝ አሁን እኮ አዞረኝ" አለች፡፡ ለጓደኛዋ መቅደስ፡፡
"አንዱን ቢራ ጨረሽው እንዴ? ትገርሚያለሽ እንደለስላሳ ነው ስልሽ እንደለስላሳ ጨለጥሽው፡፡ በይ አሁን ቀስ ብለሽ አንድ ድገሚና ከዚያ በኋላ ይበቃሻል፡፡ ለነገሩ ቢራ አንድ ስለማይጠጣ ነው እንጅ በአንድ ቢበቃሽ ጥሩ ነበር፡፡
"አሁን አመመኝ እያልኩሽ ድገሚና ጠጭ ትይኛለሽ ? ብላ ብትኮሳተርም መድገሟ አልቀረም ሁለተኛ ቢራዋን አስከፈተች፡፡
በስካር መንፈስ ምሽቱ ወደ ቀን ተቀይሮበታል፡፡ አይመሽም እንዴ? ሆቴሉ አይዘጋም? ይላል ፤ ተመስን በውስጡ ፡፡
"ከአሁን በፊት ከሴት ጋር ተኝተህ ታውቃለህ"? እንዴ አለው ያሬድ፡፡
"ከሴት ጋር መተኛት አይደለም ለመተኛትም አውርቼ አላውቅም፡፡ ዛሬ ግን ብተኛ ምን እሆናለሁ፡፡
"እና የትኛዋ ትሻልሃለች"?፡፡
"የሽሃረግ ትሻለኛለች ፤ እሽ ካለች፡፡
"እሽ ፤ እንጠይቃታለን ግን እንደ ገጠር ሴት ዝም ብለው እሽ አይሉም፡፡ ገንዘብ ይጠይቃሉ፡፡
"ለብር ችግር የለም፡፡ ብቻ እሽ አሰኝልኝ ፡፡
ያሬድ መቅደስን ለብቻዋ ጠርቶ ለማነጋገር ፈልጓል፡፡ ከመቀመጫው ተነሳ፡፡ መቅደስን ጠራት፡፡ ከሰው ጋር እንዴ? ብሎ ጠየቃት፡፡
"እኔ ከሰው ጋር ነኝ፡፡ የሽሃረግ ደግሞ እንደዚ አይነት ስራ ሰርታ ስለማታቅ አትወጣም አለችው፡፡
ደግሞ የከተማ ሴት እንደ ገጠር ነው እንዴ? በገንዘብ እሽ አትልም? ፡፡
"እሱማ ልክ ነህ ፤ እሷ ግን ስለማትሰራ ነው፡፡
ጓደኛየ ከአሁን በፊት ከሴት ጋር ተኝቶ አያውቅም፡፡ ዛሬ ምን እንደነካው እንጃ በየሽሃረግ አብዷል አላት፡፡
ብቻ ከእሷ ለመስማት እሽ ካለች እጠይቃታለሁ፡፡ ብላ ልጠይቃት እየፈራች ቢሆንም ተጠጋቻት፡፡ የሽሃረግ የጠጣችው የሐረር ቢራ አስክሯታል፡፡ ወደ ኋላ ያሰረችውን ሐር የሚመስለውን ፀጉሯን ለቃዋለች፡፡
ታዲያ አይኗን ሸፍኖት ትንሽ ትንሽ ነበር ፊቷ የሚታየው፡፡
መቅደስ የጠጣችው ቢራ እሷንም ሞቅ አድርጓት ስለነበር የሽሃረግን ሳትፈራ ስሟን አቆላምጣ የሺዬ ያሰውዬ ፎንቅቄያለሁ እያለ ነው አለቻት፡፡
"የቱ ነው"? አለች፡፡ ፀጉሯን ከፊቷ ላይ ገለጥ እያደረገች፡፡
ቢራ ከጋበዙሽ አንደኛው ፡፡ ያ የፂሙ አሪዝ የሚያምረው ሰውዬ፡፡ ደግሞ ሴት የሚባል አውጥቶ አያውቅም፡፡ ቢራ እራሱ የተማከራችሁ ይመስል እንደ አንችው ዛሬ ነው ፤ የጀመረው አለቻት፡፡
"አንች በምን አወቅሽ ዛሬ ቢራ መጀመሩን ?፡፡
አብሮት ያለው ጓደኛው ነው የነገረኝ፡፡
"እኔ እንደዚህ አይነት ስራ እንደማልሰራ እያወቅሽ ፤ ለምን ትጠይቂኛለሽ"? አለች፡፡ ውስጧ ፍራት ፍራት እየተሰማት፡፡
እሱንማ አውቃለሁ፡፡ ግን አንች እስከመቼ ድረስ ነው? ወንድ የማትፈልጊው ፤ የጠየቀሽን ሁሉ አልፈልግም እያልሽ፡፡ ላይፍሽን በአሁን ሰዓት ካልተጠቀምሽበት መቼ ልትጠቀሚበት ነው?፡፡ ደግሞ ጊዜሽ ካለፈ ወዲያ ማንም ሊጠይቅሽ አይደለም ዞር ብሎ የሚያይሽ አታገኝም፡፡ ይልቁንም ዛሬ እትዬም ስለሌለች አብረሽው እደሪ አለቻት፡፡
እሳትን በእሳት እንደ ሚባለው ሴትን በሴት አሳምኖ በቁጥጥር ስር ማድረግ በሴቶች የተለመደ መሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡
ጊዜሽ ካለፈ ዞር ብሎ የሚያይሽ አታገኝም፡፡ ያለቻት ህሊናዋን በመርፌ የተወጋች ያህል ተሰማት፡፡ በትካዜ ተዋጠች፡፡ መጀመሪያም ልቧን በአይን አፋርነቱና በጉንጩ ላይ መስመር ሰርቶ በወረደው አሪዛም ፂሙ አሸፍቶ የወሰደባት ተመስገን እንኳን ለሴት ልጅ ለወንድ ልጅ ያማልል ነበር፡፡
"እትየ ስትመጣ ካልነገርሽብኝ እኔም ወድጀዋለሁ"፡፡ አለቻት የልብ ትርታዋ ከመጠን አልፎ ቁና ቁና እያስተነፈሳት፡፡
አልነግርብሽም፡፡ ደግሞ እኔ የምናግረው ጣቱን የሚጠባ ህፃን አደረግሽኝ እንዴ ብላት "በይ አሁን
ሰውም ስለሌለ እንዘጋጋና እኔም ሰው እየጠበቀኝ ነው እንተኛ አለቻት፡፡
"እምቢ ሳትል አትቀርም አለ ፤ ያሬድ፡፡
የከተማ ሴት ገንዘብ ነው የሚፈልጉት አላልከኝም" እንዴ አለ ፤ ተመስገን፡፡
የዚች የተለየ ነው እባክህ ብሎ ሌላም ደግሞ ሳይናገር መቅደስ ጠጡና ተነሱ ልንዘጋ ነው አለች፡፡
ተመስገን መሸ እንዴ? አለ፡፡
አልታወቀህም እንዴ? ከመምሸቱም ሊነጋ ተቃርቧል፡፡ እንዴውም የእኛ ብቻ ነው፡፡
ያልተዘጋው እንጅ የሁሉም ሆቴሎች ተዘግተዋል አለች ፤ መቅደስ፡፡
"እሽ ፤ እንነሳለን ግን የሽሃረግ ምን አለችሽ"? አለ
መቅደስ በስንት ልመና እሽ አስብያታለሁ፡፡ አሁንም እየፈራች ስለሆነ እናንተ ተነሱና አልጋ ቤት ጠብቁኝ፡፡ እኔ ይዣት እመጣለሁ አለች፡፡
ተንገዳገደ፡፡ ደግፎት ወደ መኝታ ቤት ገቡ፡፡
መቅደስ ሆቴሉን ዘጋግታ ከጨረሰች በኋላ፤ የሽሃረግን የሆቴሉ ዘበኛ እንዳያያት ወደ ሽንት ቤት የሚሄዱ አስመስላ ወደ እነ ያሬድ አልጋ ቤት አስገባቻት፡፡ ያሬድ ለሚተኛበት ሌላ አልጋ ከፍታለት አብሯት ወደ ሚያድረው ሰው ጋር ተመለሰች ፡፡
ለተመስገን ችግር የሚያጋጥምህ ከሆነ እዚህኛው አልጋ ቤት ነው የምተኛው፡፡ ነገ በጥዋት ወደ አቶ ላንቻ ቤት እንሄዳለን ብሎት ሁለተኛ ወደ ያዘው አልጋ ሄዶ ተኛ፡፡
የመኝታው በር ተዘጋ፡፡ ልብሳቸውን አወላለቁ፡፡ ከአሁን በፊት እንደሚተዋወቁ ፍቅረኛ ተቃቀፉ፡፡ ታምሪያለሽ ፤ አንተም ታምራለህ፡፡ ብቻ የሚል ቃል ተነጋግረው በለበሱት ብርድልብስ ውስጥ ከንፈር ለከንፈር ተፈላልገው ተገናኙ፡፡
የሁለቱም የሰውነት ሙቀት ጨመረ፡፡ ሳይታወቃቸው የተመስገን እግሮች በየሻረግ እግሮች ውስጥ ተጠላለፉ፡፡ በስካር መንፈስ ጉዳያቸውን ከፈፀሙ በኋላ ሁለቱም እራሳቸውን ሳቱ፡፡ መተቃቀፉና መሳሳሙ ቀረ፡፡ ድጋሜም አልተገናኙም፡፡ የለሊቱ ጨለማ ለቆ የቀኑ ብርሃን ተተካ፡፡
ያሬድ እሱም በስካር መንፈስ የመኝታ በሩን ከፍቶ እንደ ገባ ጫማውን እንኳን አላወለቀም፡፡ የወደቀበትን አያውቀም፡፡ ስካርና እንቅልፉን አሳልፎ ከተኛበት መኝታ ላይ ባነነ፡፡ ጫማውን ሳያወልቅ በመተኛቱ ተገረመ፡፡እንደዚህ እራሴን እስከምስት ድረስ ሰክሬ ኖሯል፡፡ ወይ ነዶ የሰውዬው ልጅ እያለ ተነሳ፡፡ በሩን ከፈተ፡፡ ሌሊቱ ነግቶ ቀን ቀን እየሸተተ ነው፡፡
የስካር ፊቱን ታጠበ፡፡ ልቡ አቶ ላንቻ ጋር ለመሄድ ተቻኩሏል፡፡ የአልጋው በር አልተዘጋም፡፡ ገርበብ ብሏል፡፡ ሳይዘጉት ይሆን እንዴ? የተኙት እያለ ገርበብ ያለውን በር ከፈት አድርጎ ገባ፡፡
የሽሃረግ ከተኛችበት ስትነሳ ከማታውቀው ሰው ጋር ተኝታ የንፅህና ክብሯን በመስጠቷ የሞት ያህል ተሰምቷታል፡፡ በሁለት እጆቿ እራሷን ደግፋ ከአንገቷ ወደ መሬት አቀርቅራ ከመኝታው ላይ ተቀምጣለች፡፡ የተፈጠረውንና ያደረገችውን ሁሉ ለማስታወስ እየሞከረች ከህሊናዋ ጋር እየተሟገተች ሳለ ያሬድ በር ከፍቶ ገባ፡፡ ካቀረቀረችበት ቀና አለች፡፡ ከያሬድ ጋር አይን ለአይን ተጋጩ፡፡ ያሬድ ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡ ድንጋጤ ተሰማው፡፡
የሽሃረግን ደጋግሞ አትኩሮ ተመለከታት፡፡ ማታ በዲም ላይትና በፌር ቅባት ህንዳዊ መስላ የታየችው የፊት ላይ ቅባት ተወግዶ የኢትዮጵያዊነት ደም ግባቷ ተመልሷል፡፡ የጠይም ለግላጋ ቆንጆ መሆኗን በደንብ ይታያል፡፡ የሚያውቃት የሚያውቃት መሰለው፡፡
ተመስገን የት እንደ ሄደ እንኳን አልጠየቃትም፡፡ ወደ ተቀመጠችበት መኝታ ተጠጋ፡፡
ምነው? የማውቅሽ መሰለኝ፡፡ ግን ስምሽ ትክክለኛ የሽሃረግ ነው? አላት፡፡
የሽሃረግ ጭንቅላቷን በመጥረቢያ እንደተመታች ያህል ባለችበት ክው ብላ ቀረች፡፡ ያሬድን አፍጣ ፣ ደግማ ፣ ደጋግማ አየችው፡፡
"የየየየየየየየየየየየየ..ታ...ውቀኛለህ"? አለች፡፡ አፏ እየተንተባተበ፡፡
👍69❤3
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ጭንቅ
ደጅ ፣ ደጁን አስሬ እየወጣች ትመለከታለች፡፡ የጣደችውን ቡና እየተንተከተከ ሳታነሳው አራት ሰዓት ሆነው፡፡
በህሊናዋ የተለያየ ሃሳብ እየተመላለሰ ረብሿታል፡፡ ምን ገጥሟቸው ይሆን ? እንዴው መኪና ተገልብጦ ይሆን? ከሰው ተጣልተው ይሆን? ነጋዴው አልመጣላቸው ይሆን ? ጥሩውንም መጥፎውንም ልቧ የገመተውንም ሁሉ እያወጣች እያወረደች ከራሷ ሃሳቧ ትሟገታለች፡፡
ኮሽ ባለቁጥር እየወጣች እየገባች እንቅልፍ የሚባል በአይኗ ሳይዞር ከአሁን አሁን ይመጣሉ እያለች ሌሊቱን ሳታምነው ቁጭ ብላ የማደር ያህል አነጋች፡፡ ጭንቀቱ ውሎም አድሮም አልተፋታትም፡፡
ተመስገንና ያሬድ ወሬያቸው እና ብቅታቸውም ሳይታይ ቀናት ተቆጠሩ፡፡
ተመስገንና ያሬድ ወሬያቸው እና ብቅታቸውም ሳይታይ ቀናት ተቆጠሩ፡፡
አበበች ሃሳብና ጭንቀቷ እየባሰባት ቢሄድም መፍትሄ አላገኘችም፡፡ ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡
የቻለው አባት አለች፡፡ አቶ ጎሹን በበራቸው ላይ ከብቶች ይዘው ሲያልፉ ድንገት አይታ፡፡ ታዲያ አቶ ጎሹን የቻለው አባት ብላ መጣራቷ በልጃቸው ስም ስለምጠራቸው ነበር፡፡
አቶ ጎሹ የቻለው አባት ወደ አለው ድምፅ መለስ አሉ፡፡ "ጠራሽኝ ልበል" ? አሉ ፤ ለአበበች፡፡
አዎ ፤ እኔ ነኝ የጠራዎት፡፡ ብላ ቀኑም እረፍዶ ስለነበር ሰላም አረፈዱ የቻለው አባት" አለች፡፡
"ሰላም አረፈድሽ አበበች፡፡ ምነው ደህና አይደለሽም ኖሯል? አሏት፡፡ አይን አይኗን እየተመለከቱ፡፡
"አይ! እኔ እንኳን ደህናነኝ፡፡ ባለቤቴ ከተመስገን ጋር ውሎ ገባ እንመለሳለን ብለው ወደ ድሬደዋ ሄደው ነበር፡፡ ይኸው ውሎ ገባ ሳይመለሱ ሰነበቱ፡፡ አሁንም ብቅታቸውም ጠፋ፡፡ እንዴው የማደርገው ሲጠፋኝ ነው፡፡ እርሶዎን የጠራዎት" አለች፡፡ መሬት መሬት እየተመለከተች፡፡
አቶ ጎሹ ታዲያ ምን ይሆናሉ ብለሽ ነው፡፡ መኪና አጥተው ሊሆን ይችላል፡፡ ወይም የሄዱበት ሳይሳካላቸው ቀርቶ አድረው ለመምጣት አስበው ይሆናል፡፡ ለማንኛውም ምንም ማሰብ ፣ መጨነቅ የለብሽም፡፡ ደግሞ ወንድ ልጆች ናቸው፡፡ አድረው ይገኛሉ፡፡ ሴት ልጆች ቢሆኑ እንኳን አድረው አይገኙም ይባላል፡፡ ማታ ሊመጡ ይችላሉ ብለው አፅናንተዋት ወደ ከብቶቻቸው ተመለሱ፡፡
አበበች የመለሱላትን የማፅናኛ መልስ በትንሹም ቢሆን ለመረጋጋት ሞክራ መኪና አጥተው ሊሆን ይችላል፡፡ ወይም ነጋዴው ሳይመጣ ቀርቶ ሰንብተው ይሆናል፡፡ ብላ በማሰብ ተመልሳ ወደ ቤቷ ገባች ፡፡
አበበች ማታ ይመጣሉ እያለች ስትጠብቅ የሷ ማታ ሳያልቅ ማታና ማታ ተደምሮ አምስት ማታ ቢሆንም እንኳን ያሬድና ተመስገን ሊመጡ አይደለም አየናቸው የሚል ሳታገኝ..ቆየች
ህልምነው ቅዠት ;
"አዎ ፤ ነግቷል ወፍ እየተንጫጫ ነው፡፡ ምነው ሰላም አላደርሽም እንዴ? አሉ፡፡ ቄስ መልካሙ ለባለቤታቸው፡፡ በሌሊት ተነስተው ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ እየተነሳሱ፡፡
"እንዴው ዛሬ ደግሞ ሲያቃዠኝ ነው ያደረው" አሉ ፤ ቄስ
"ኧረ ! እኔንም ሲያቃዠኝ ነው ያደረው፡፡ ያ ተመስገን ደህና አይደል ይሆን? ከያሬድ ጋር የምንሄድበት አለ ብሎኝ ነበር የሄደው፡፡ ማታ ይመጣል ብዬ ጠብቄው ነበር፡፡ ይሄው ሳይመጣ ዛሬ አምስት ቀኑን ያዘ" አሉ፡፡ አይናቸውን በሸማቸው እየጠራረጉ፡፡
"ከያሬድ ጋር ከሄደ ምን ይሆናል ፤ ብለሽ ነው?፡፡ ያሬድ ነጋዴም አይደል ፤ ምን አልባት አብሮት ይዞት ሄዶ ሊሆን ይችላል፡፡ ለማንኛውም እመቤቴ እንደፍቃዷ፡፡ እንግዴህ ቼር ነገር ታሰማን ፡፡ ዛሬ ደግሞ ተረኛ ገቢ ነኝ፡፡ ለቅዳሴ ሳይረፍድብኝ ልሂድ ፤ አንችም ተመስገን ካልመጣ ለከብቶቹ የሚበላ ፤ የታሰሩበት ስጫቸው፡፡ ስመለስ ውሃ አጠጣቸዋለሁ፡፡ ብለው ነጠላቸውን ለባብሰው ፤ ዘንጋቸውን ይዘው ፣ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሄዱ፡፡
"እንዴው ዛሬ ደግሞ ምን ልታሰማኝ ይሆን ? ውስጤ የሚረበሸው ፣ እንግዴህ እመብርሃን አንች ታውቂያለሽ ፡፡ ያለዐንች ማን አለኝ እያሉ የጥዋት ፀሎታቸውን በቤታቸው የእንጨት ምሰሶ ስር በፊታቸው ተደፍተው የሚወዷትን የአገራቸውን ታቦት ጥሩ ነገር እንድ ታሰማቸው ተማፀኑዋት፡፡
ከተንበረከኩበት የእንጨት ምሰሶ ስር ተነሱ፡፡ ቤታቸውን በዶዶሆ ቅጠል ጠረግ ፣ ጠረግ አደረጉ፡፡ የሳር ድርቆሽ ከዓውድማ አምጥተው ለከብቶቻቸው ሰጡ፡፡ ሲያቃዣቸው ያደረውን ህልም ይሁን ቅዠት በሃሳባቸው እያወጡ እያወረዱ ለመፍታት ይግተረተራሉ፡፡ አንዴ በጥሩ ፣ አንዳንዴ በመጥፎ ፣ እየፈቱ እንደገና ደግሞ ህልም እንደፈችው ነው እያሉ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ይከራከራሉ፡፡
ታዲያ ወ/ሮ አሰገደች ሳይታወቃቸው ሰዓቱ እረፍዷል፡፡ ቁርስ እንኳን ሳይቀምሱ ባለቤታቸው ከቤተክርስቲያን የመምጫቸው ሰዓት ተቃርቧል፡፡
ቄስ መልካሙ ከቅዳሴ እንደ ወጡ ዛቲ ቀምሰው ለምዕመናኑ አሳርገው ፣ ከብቶቻቸውን ውሃ የሚያጠጣላቸው ስለሌለ ፣ እንዳይረፍድባቸው ሰንበቴያቸውን ቀምሰው ገበታ እንደተነሳ ተነስተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ከብቶቻቸው ከማሰሪያቸው ሳይፈቱ ደረሱ፡፡ የተሰጣቸውን የሳር ድርቆሽ መብላታቸውን ትተው ቆመዋል፡፡ ያ! ተመስገን አልመጣም ማለት ነው፡፡ ቢመጣ ከብቶቹን ውሃ ያጠጣቸው ነበር እያሉ ወደ ቤት ገቡ፡፡
"ዛሬ ደግሞ ሰንበቴ ሳትገባ ነው እንዴ የመጣኸው"? አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡
"አልቆየሁም ፤ እንጅ ደረስ ብያለሁ፡፡ ከቅዳሴም ስንወጣ አረፈድን ፤ ዝክርና ክርስትና ስለነበር ፤ሰንበቴ ቶሎ አልገባንም፡፡ ብለው ተመስገን አልመጣም እንዴ"? አሉ፡፡
"እስከ አሁን አልመጣም፡፡ እኔም አበበች ጋር ሄጀ እጠይቃለሁ ብዬ ነበር፡፡ ከቤትም ሳልወጣ እየተንደፋደፍኩ ምንም የረባ ስራ እንኳን ሳልሰራ አንተም መጣህ"፡፡
ከብቶቹን ላጠጣና እስከምመለስ ካልመጣ አይተን እኔ አበበች ጋር ሄጄ እጠይቃታለሁ፡፡ ብለው ከብቶቻቸውን ከታሰሩበት ፈትተው ውሃ ለማጠጣት ወደ ወንዝ ወረዱ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ባለቤታቸው ከወንዝ እስኪመለሱ ቡና አፍልተው ጠበቋቸው፡፡
ከብቶቻቸውን አጠጥተው ተመለሱ፡፡ የጤፍ ጭድ የሚበላ ሰተው ፈልቶ የጠበቃቸውን ቡና ከባለቤታቸው ጋር እየጠጡ ነው፡፡
እንዴው ያ! ማንደፍሮ የሚሸጥ ባህርዛፍ አለ ብሎኝ ነበር፡፡ ጠዋት ቤተ ክርስቲያን አግኝቸው እጠይቀዋለሁ ብዬ ሳልጠይቀው እረሳሁት፡፡ አሁን ደረስ ብዬ ልምጣ መሰለኝ ፡፡
"እንዴ! ቅድም አበበች ጋር ሄጀ እመጣለሁ አላልከኝም?፡፡ እማንደፍሮ ጋር በሌላ ቀን አይደርስም"? አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡
"ምን ያህል እቆያለሁ፡፡ በቁሜ ደረስ ብዬ የሚሸጠውን ባህርዛፍ አይቼ ቶሎ ስመለስ እሄዳለሁ፡፡
ታዲያ ቄስ መልካሙ ባለቤታቸው ያሉትን ለጊዜው ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው ተነስተው ወደ ማንደፍሮ ቤት አቀኑ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ከአዳራቸው አንስተው ቀኑን ሁሉ ውስጣቸው ሲረበሽ መዋሉ እረብሿቸዋል፡፡ ልጀ ምን ሆኖ ይሆን ? እንዴው ከቤት እንኳን ወጥቶ አያውቅ፡፡ ከያሬድ ጋር ከተማ መሃል ተጠፋፍተው ይሆን ? ክልብ ክልብ ሲል መኪና ባልገጨብኝ ብቻ፡፡
ለአስር ዓመታት የተለየቻቸውን ብርቅየ የአንጀታቸው ክፋይ የሆነችው ልጃቸውን እድላዊትን ወደ ኋላ፤ ተመልሰው አስታወሱ፡፡ እንባቸው በሁለቱም አይኖቻቸው ግጥም አለ፡፡ ለመመለስ በውስጥ
ቀሚሳቸው ጠራርጉት፡፡ ከአንጀታቸው የመጣ እንባ መመለስ ግን አቃታቸው፡፡ በተቀመጡበት እንደ እንኳይ ኮለል እያለ እንባቸው ይዘረገፍ ጀመር፡፡
ቄስ መልካሙ ቆይተው ለአይን ያዝ ሲያደርግ ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ጭንቅ
ደጅ ፣ ደጁን አስሬ እየወጣች ትመለከታለች፡፡ የጣደችውን ቡና እየተንተከተከ ሳታነሳው አራት ሰዓት ሆነው፡፡
በህሊናዋ የተለያየ ሃሳብ እየተመላለሰ ረብሿታል፡፡ ምን ገጥሟቸው ይሆን ? እንዴው መኪና ተገልብጦ ይሆን? ከሰው ተጣልተው ይሆን? ነጋዴው አልመጣላቸው ይሆን ? ጥሩውንም መጥፎውንም ልቧ የገመተውንም ሁሉ እያወጣች እያወረደች ከራሷ ሃሳቧ ትሟገታለች፡፡
ኮሽ ባለቁጥር እየወጣች እየገባች እንቅልፍ የሚባል በአይኗ ሳይዞር ከአሁን አሁን ይመጣሉ እያለች ሌሊቱን ሳታምነው ቁጭ ብላ የማደር ያህል አነጋች፡፡ ጭንቀቱ ውሎም አድሮም አልተፋታትም፡፡
ተመስገንና ያሬድ ወሬያቸው እና ብቅታቸውም ሳይታይ ቀናት ተቆጠሩ፡፡
ተመስገንና ያሬድ ወሬያቸው እና ብቅታቸውም ሳይታይ ቀናት ተቆጠሩ፡፡
አበበች ሃሳብና ጭንቀቷ እየባሰባት ቢሄድም መፍትሄ አላገኘችም፡፡ ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡
የቻለው አባት አለች፡፡ አቶ ጎሹን በበራቸው ላይ ከብቶች ይዘው ሲያልፉ ድንገት አይታ፡፡ ታዲያ አቶ ጎሹን የቻለው አባት ብላ መጣራቷ በልጃቸው ስም ስለምጠራቸው ነበር፡፡
አቶ ጎሹ የቻለው አባት ወደ አለው ድምፅ መለስ አሉ፡፡ "ጠራሽኝ ልበል" ? አሉ ፤ ለአበበች፡፡
አዎ ፤ እኔ ነኝ የጠራዎት፡፡ ብላ ቀኑም እረፍዶ ስለነበር ሰላም አረፈዱ የቻለው አባት" አለች፡፡
"ሰላም አረፈድሽ አበበች፡፡ ምነው ደህና አይደለሽም ኖሯል? አሏት፡፡ አይን አይኗን እየተመለከቱ፡፡
"አይ! እኔ እንኳን ደህናነኝ፡፡ ባለቤቴ ከተመስገን ጋር ውሎ ገባ እንመለሳለን ብለው ወደ ድሬደዋ ሄደው ነበር፡፡ ይኸው ውሎ ገባ ሳይመለሱ ሰነበቱ፡፡ አሁንም ብቅታቸውም ጠፋ፡፡ እንዴው የማደርገው ሲጠፋኝ ነው፡፡ እርሶዎን የጠራዎት" አለች፡፡ መሬት መሬት እየተመለከተች፡፡
አቶ ጎሹ ታዲያ ምን ይሆናሉ ብለሽ ነው፡፡ መኪና አጥተው ሊሆን ይችላል፡፡ ወይም የሄዱበት ሳይሳካላቸው ቀርቶ አድረው ለመምጣት አስበው ይሆናል፡፡ ለማንኛውም ምንም ማሰብ ፣ መጨነቅ የለብሽም፡፡ ደግሞ ወንድ ልጆች ናቸው፡፡ አድረው ይገኛሉ፡፡ ሴት ልጆች ቢሆኑ እንኳን አድረው አይገኙም ይባላል፡፡ ማታ ሊመጡ ይችላሉ ብለው አፅናንተዋት ወደ ከብቶቻቸው ተመለሱ፡፡
አበበች የመለሱላትን የማፅናኛ መልስ በትንሹም ቢሆን ለመረጋጋት ሞክራ መኪና አጥተው ሊሆን ይችላል፡፡ ወይም ነጋዴው ሳይመጣ ቀርቶ ሰንብተው ይሆናል፡፡ ብላ በማሰብ ተመልሳ ወደ ቤቷ ገባች ፡፡
አበበች ማታ ይመጣሉ እያለች ስትጠብቅ የሷ ማታ ሳያልቅ ማታና ማታ ተደምሮ አምስት ማታ ቢሆንም እንኳን ያሬድና ተመስገን ሊመጡ አይደለም አየናቸው የሚል ሳታገኝ..ቆየች
ህልምነው ቅዠት ;
"አዎ ፤ ነግቷል ወፍ እየተንጫጫ ነው፡፡ ምነው ሰላም አላደርሽም እንዴ? አሉ፡፡ ቄስ መልካሙ ለባለቤታቸው፡፡ በሌሊት ተነስተው ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ እየተነሳሱ፡፡
"እንዴው ዛሬ ደግሞ ሲያቃዠኝ ነው ያደረው" አሉ ፤ ቄስ
"ኧረ ! እኔንም ሲያቃዠኝ ነው ያደረው፡፡ ያ ተመስገን ደህና አይደል ይሆን? ከያሬድ ጋር የምንሄድበት አለ ብሎኝ ነበር የሄደው፡፡ ማታ ይመጣል ብዬ ጠብቄው ነበር፡፡ ይሄው ሳይመጣ ዛሬ አምስት ቀኑን ያዘ" አሉ፡፡ አይናቸውን በሸማቸው እየጠራረጉ፡፡
"ከያሬድ ጋር ከሄደ ምን ይሆናል ፤ ብለሽ ነው?፡፡ ያሬድ ነጋዴም አይደል ፤ ምን አልባት አብሮት ይዞት ሄዶ ሊሆን ይችላል፡፡ ለማንኛውም እመቤቴ እንደፍቃዷ፡፡ እንግዴህ ቼር ነገር ታሰማን ፡፡ ዛሬ ደግሞ ተረኛ ገቢ ነኝ፡፡ ለቅዳሴ ሳይረፍድብኝ ልሂድ ፤ አንችም ተመስገን ካልመጣ ለከብቶቹ የሚበላ ፤ የታሰሩበት ስጫቸው፡፡ ስመለስ ውሃ አጠጣቸዋለሁ፡፡ ብለው ነጠላቸውን ለባብሰው ፤ ዘንጋቸውን ይዘው ፣ ወደ ጉራንባ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሄዱ፡፡
"እንዴው ዛሬ ደግሞ ምን ልታሰማኝ ይሆን ? ውስጤ የሚረበሸው ፣ እንግዴህ እመብርሃን አንች ታውቂያለሽ ፡፡ ያለዐንች ማን አለኝ እያሉ የጥዋት ፀሎታቸውን በቤታቸው የእንጨት ምሰሶ ስር በፊታቸው ተደፍተው የሚወዷትን የአገራቸውን ታቦት ጥሩ ነገር እንድ ታሰማቸው ተማፀኑዋት፡፡
ከተንበረከኩበት የእንጨት ምሰሶ ስር ተነሱ፡፡ ቤታቸውን በዶዶሆ ቅጠል ጠረግ ፣ ጠረግ አደረጉ፡፡ የሳር ድርቆሽ ከዓውድማ አምጥተው ለከብቶቻቸው ሰጡ፡፡ ሲያቃዣቸው ያደረውን ህልም ይሁን ቅዠት በሃሳባቸው እያወጡ እያወረዱ ለመፍታት ይግተረተራሉ፡፡ አንዴ በጥሩ ፣ አንዳንዴ በመጥፎ ፣ እየፈቱ እንደገና ደግሞ ህልም እንደፈችው ነው እያሉ ከራሳቸው ሃሳብ ጋር ይከራከራሉ፡፡
ታዲያ ወ/ሮ አሰገደች ሳይታወቃቸው ሰዓቱ እረፍዷል፡፡ ቁርስ እንኳን ሳይቀምሱ ባለቤታቸው ከቤተክርስቲያን የመምጫቸው ሰዓት ተቃርቧል፡፡
ቄስ መልካሙ ከቅዳሴ እንደ ወጡ ዛቲ ቀምሰው ለምዕመናኑ አሳርገው ፣ ከብቶቻቸውን ውሃ የሚያጠጣላቸው ስለሌለ ፣ እንዳይረፍድባቸው ሰንበቴያቸውን ቀምሰው ገበታ እንደተነሳ ተነስተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ከብቶቻቸው ከማሰሪያቸው ሳይፈቱ ደረሱ፡፡ የተሰጣቸውን የሳር ድርቆሽ መብላታቸውን ትተው ቆመዋል፡፡ ያ! ተመስገን አልመጣም ማለት ነው፡፡ ቢመጣ ከብቶቹን ውሃ ያጠጣቸው ነበር እያሉ ወደ ቤት ገቡ፡፡
"ዛሬ ደግሞ ሰንበቴ ሳትገባ ነው እንዴ የመጣኸው"? አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡
"አልቆየሁም ፤ እንጅ ደረስ ብያለሁ፡፡ ከቅዳሴም ስንወጣ አረፈድን ፤ ዝክርና ክርስትና ስለነበር ፤ሰንበቴ ቶሎ አልገባንም፡፡ ብለው ተመስገን አልመጣም እንዴ"? አሉ፡፡
"እስከ አሁን አልመጣም፡፡ እኔም አበበች ጋር ሄጀ እጠይቃለሁ ብዬ ነበር፡፡ ከቤትም ሳልወጣ እየተንደፋደፍኩ ምንም የረባ ስራ እንኳን ሳልሰራ አንተም መጣህ"፡፡
ከብቶቹን ላጠጣና እስከምመለስ ካልመጣ አይተን እኔ አበበች ጋር ሄጄ እጠይቃታለሁ፡፡ ብለው ከብቶቻቸውን ከታሰሩበት ፈትተው ውሃ ለማጠጣት ወደ ወንዝ ወረዱ ፤ ቄስ መልካሙ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ባለቤታቸው ከወንዝ እስኪመለሱ ቡና አፍልተው ጠበቋቸው፡፡
ከብቶቻቸውን አጠጥተው ተመለሱ፡፡ የጤፍ ጭድ የሚበላ ሰተው ፈልቶ የጠበቃቸውን ቡና ከባለቤታቸው ጋር እየጠጡ ነው፡፡
እንዴው ያ! ማንደፍሮ የሚሸጥ ባህርዛፍ አለ ብሎኝ ነበር፡፡ ጠዋት ቤተ ክርስቲያን አግኝቸው እጠይቀዋለሁ ብዬ ሳልጠይቀው እረሳሁት፡፡ አሁን ደረስ ብዬ ልምጣ መሰለኝ ፡፡
"እንዴ! ቅድም አበበች ጋር ሄጀ እመጣለሁ አላልከኝም?፡፡ እማንደፍሮ ጋር በሌላ ቀን አይደርስም"? አሉ ፤ ወ/ሮ አሰገደች፡፡
"ምን ያህል እቆያለሁ፡፡ በቁሜ ደረስ ብዬ የሚሸጠውን ባህርዛፍ አይቼ ቶሎ ስመለስ እሄዳለሁ፡፡
ታዲያ ቄስ መልካሙ ባለቤታቸው ያሉትን ለጊዜው ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው ተነስተው ወደ ማንደፍሮ ቤት አቀኑ፡፡
ወ/ሮ አሰገደች ከአዳራቸው አንስተው ቀኑን ሁሉ ውስጣቸው ሲረበሽ መዋሉ እረብሿቸዋል፡፡ ልጀ ምን ሆኖ ይሆን ? እንዴው ከቤት እንኳን ወጥቶ አያውቅ፡፡ ከያሬድ ጋር ከተማ መሃል ተጠፋፍተው ይሆን ? ክልብ ክልብ ሲል መኪና ባልገጨብኝ ብቻ፡፡
ለአስር ዓመታት የተለየቻቸውን ብርቅየ የአንጀታቸው ክፋይ የሆነችው ልጃቸውን እድላዊትን ወደ ኋላ፤ ተመልሰው አስታወሱ፡፡ እንባቸው በሁለቱም አይኖቻቸው ግጥም አለ፡፡ ለመመለስ በውስጥ
ቀሚሳቸው ጠራርጉት፡፡ ከአንጀታቸው የመጣ እንባ መመለስ ግን አቃታቸው፡፡ በተቀመጡበት እንደ እንኳይ ኮለል እያለ እንባቸው ይዘረገፍ ጀመር፡፡
ቄስ መልካሙ ቆይተው ለአይን ያዝ ሲያደርግ ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
👍64❤11👏2
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
የማን ይሁን ?
የባሰ! እሾክና መርፌ ተነቅሎ የማይጣል፤ በቅርብ ሳይገፋ ያልተደረሰበት ፤ ከላይኛው የወረደ ዱብዳ ፤ የፈጣሪ የቁጣ ስጦታ፡፡ ለማን ታድርገው? ለማን ትስጠው? ለማንስ አቤት ትበል? ተቆርጦ የማይጣል የጣት ቁስል ሆነባት፡፡
ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረ፡፡ እንደ ተዳፈነ እሳት ውስጧን አቃጠለው፡፡ እንደ ሰኔ ደመና አረምሞ ገፍቷል፡፡ በአንድ ቀን ስህተት የእግዚአብሔር ስራ እንኳን ባይባልም በመቅሰፍቱ በዲያቢሎስ ቅንብር ሆዷ ውፍረትን መከታ እና ከለላ ተጠቅሞ ሳይታወቃት እየገፋ መጥቷል፡፡
እድላዊት ከወንድሟ ከተመስገን ፀንሳለች፡፡ በአንድ እንዴት ላረግዝ እችላለሁ?፡፡ ስታዝን ስትጨነቅ ዘጠኝ ወር ተቆጥሮ ቦርጩ ወደ ልጅ ተቀየረ፡፡ ወንድ ልጅ ከነ ቃጭሉ ተገላገለች፡፡ ግን ከፊቷ አሁንም የማይገፋ ከዳቢሎስ የተገነባ የጨለማ ተራራ ተጋርዶባታል፡፡
ምንጃር ሸንኮራ አውራጃ ውስጥ ነው፡፡ ጉራንባ ማርያም አካባቢ ያለ ማህበረሰብ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡ በእምነታቸው አክራሪና ከእምነት ውጭ ለሚከሰቱ ማንኛውም የክርስትና ጥፋት የፈፀመ ከማህበረሰቡ ይገለላል፡፡ እንደ እድር ፣ ባልትና እና ማህበር የመሳሰሉትን መካፈል አይችልም፡፡ በማህበረሱቡ የተጠላ ፤የማይወደድ ፣ ከሰው እንዳልተፈጠረ ከሰው ውጭ ተደርጎ ይቆጠራል።
እድላዊት እያወቀች ሳይሆን ሳታውቅ ከወንድሟ ከተመስገን መውለዷን ከያሬድ ውጭ ማንም አያውቅም፡፡
የወለደችውን ልጅ ክርስትና የሚነሳው የወላጅ አባት ስም ካልታወቀ መነሳት ፤ መጠመቅ የተወገዘና የተከለከለ ነው፡፡ የእድላዊት ልጅ ባለማወቅ አባት ታዲያ ማን ይሁን ? የማንስ ተብሎ ክርስትና ይጠመቅ ? አክ ተብሎ የተተፋ ምራቅ ተመልሶ አይዋጥ፡፡ የተመስገን ብትለው ለእሷ አንዴ ሞት ቢሆንም ለዘመዶቿና ለቤተሰቦቿ አስሬ ሞት ብቻ
ሳይሆን ከሰው እንዳልተፈጠሩና ወግ አጥባቂ የክርስትና አገልጋይ እንዳልሆኑ ከሰው ውጭ ተደርገው እንደሚገለሉ የሚታወቅ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡
ታዲያ እድላዊት ይህ ሁሉ የታዘለባትን የጭንቀት እሳት ማማከር ያለባት ለወንድሟ ለተመስገን እንጅ ለማንም ማማከር እንደ ማይቻል ግልፅ ነው፡፡ ግን አሁንም ሌሊቱ ጨልሞባታል፡፡
"ምን እናድርግ ? የልጁ የክርስትና ቀን እየደረሰ ነው፡፡ እኔ ጨንቆኛል፡፡ የማደርገው ጠፍቶኛል፡፡ ከእንግዴህ ያለኝ አማራጭ መርዝ ጠጥቸ ወይም ታንቄ መሞት ነው፡፡ የወንድሜ ነው ብየ ክርስትና አላስነሳም፡፡ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡
ተመስገን የእህቱ ጭንቀት በሱም ላይ ካደረበት እና ከሰነበተበት ቆይቷል፡፡ ጥሎ እንዳይጠፋ እድላዊትን ተመልሶ ዳግመኛ የማያገኛት መሰለው፡፡
እድላዊት እያለቀሰች መልስ እንኳን ሳይሰጣት ከያሬድ ጋር ደርሸ መጣሁ ብሏት ተነስቶ ወደ ያሬድ ቤት ሄደ፡፡
ተመስገን እንደደረሰ ከያሬድ ጋር የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ ያሬድ ወደ እርሻ ሊሄድ ሞፈርና ቀንበር እያዘጋጀ ነው፡፡
"ወደ እርሻ ልትሄድ ነው እንዴ ሞፈርና ቀንበር የምታሰናዳው?" አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አዎ፤ እንዴው ትንሽ የፋልማ መሬት ከሰም ነበረኝ፡፡ ቧጠጥ አድርጌያት ልምጣ ብዬ ነበር አነሳሴ፡፡ ስተረካከም እዚሁ እረፈደ ብሎ ወደ ቤት ግባ እንጅ አለው፡፡
"ኧረ አልገባም፡፡ አንተ ጋር ነበር የመጣሁት"፡፡
"ምነው በደህና ነው"? አለ ፤ ያሬድ፡፡
"ምን ደህንነት አለ ፤ ገና ስፈጠር የአርባ ቀን እድሌ በእሳት ተሞልቶ የእሳት እረመጡ ወደ ጭስነት ተቀይሮ የመውጭያ በር አጥቶ በቁሜ እያቃጠለኝ፡፡
"ምነው እድላዊት ሰላም አይደለችም እንዴ?፡፡
"አይ! ተወኝ ፤ አሁን የእድላዊት ነገር አስጨንቆኛል፡፡ የልጁ ክርስትና እየደረሰ ነው፡፡ የአባቱ ስም ካልታወቀ ክርስትና እንደ ማይጠመቅ አንተም ታውቃለህ፡፡
የማደርገው ሁሉ ግራ ገብቶኛል፡፡ ወንድሜ እባክህ ከዚህ ጨለማ አውጣኝ፡፡ ያላንተ ማንም የማዋየውና የማማክረው የለኝም አለው፡፡በሃዘን ተሞልቶ ፡፡
"በምን ልርዳህ የማደርገው ጠፍቶኝ እኮ ነው፡፡ እስከ አሁንም ዝም ያልኩህ እንጅ እኔ እንኳን ወደ አዲስ አበባ ይዘናት እንድንሄድ አስቤ ነበር፡፡ ግን ክርስትና ሳታስነሳ ከቤት መውጣት አይቻልም ብየ ነው፡፡ አሁን በምን ላግዛችሁ ? ንገረኝና በተቻለኝ አቅም ልሞክር አለ፡፡
በፊቱ ላይ ወርዶ ቡሃቃ ያስመሰለውን እንባ በለበሰው ፎጣ እየጠራረገ እኔማ ለመጥፋትም አስቤ ነበር፡፡ ግን እድላዊት ጥሎ የሚሄድ አንጄት አጣሁ፡፡ አሁን አንተን የማስቸግርህ ልጁ ክርስትና እስከሚነሳ ድረስ የአባቱን ስም በአንተ እናድርግና ክርስትና ከተጠመቀ በኋላ ፤ የተፈጠረውንና የተደረገውን ባለመተዋወቅ እንደ ሆነ ለቤተሰብ እንነግራለን አለ፤ ተመስገን ፡፡ ደፍሮ በመናገሩ አይኑን ላለማየት አቀርቅሮ መሬት መሬት እያየ፡፡
የልጁ አባት ሆኘ ክርስትና ቢጠመቅ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን የአካባቢያችንን ባህል እንደምታውቀው በሚስቱ ላይ ዲቃላ ወልዷል ተብየ እኔ ከማህበረሰብ እንደምገለል፡፡ ደግሞም ባለቤቴ ይህንን ስሰማ በእኔ ላይ ዲቃላህን ታንጠባጥባለህ ብላ ባዶቤት ዘግታብኝ ትሄዳለች አለ ፤ ያሬድ፡፡
"ያልከው ሁሉም ይገባኛል፡፡ ግን ከወንድሟ ወለደች ቢባል ምን ያህል እንደሚከብድ መገመት አያቅትህም፡፡ ደግሞ አባታችን በዚህ ቦታ ወግ አጥባቂ እንደ ሆነ ታውቃለህ፡፡
እባክህ! ያሬድ ስለፈጠረህ አምላክ! ተለመነኝ ሳላውቅ እንደ ሆነ እሳት ውስጥ የገባሁት አንተም ታውቃለህ፡፡ ሚስጥሩን ለባለቤትህ እንነግራታለን፡፡ መጀመሪያ አንተ ብቻ እሽ በለኝ፡፡ እያለቀሰ ተማፀነው፡፡
ያሬድ የሚለው ሁሉ ጨነቀው፡፡ የእድላዊትና የተመስገን ስቃና መከራ የሱም ሆነ፡፡ ክርስትናው እስከሚያልፍ የልጁ አባት ለመሆን ብቻውን መወሰን አልቻለም፡፡
"ለማንኛውም አበበችን አብረን ሚስጥሩን እናካፍላትና እሷ እሽ ካለች የእኔ አያስቸግርም፡፡ አይቻልም ካለች ግን ምንም ላደርግ አልችልም" አለው
"እሽ አንተ እንዳልክ" ብሎት ወደ ቤት ገቡ፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች" ? አለ ፤ ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርክ ተመስገን" ? አለች ፤ አበበች፡፡
ጉንጮቹ አብጠው ገና በጥዋቱ አይኖቹ ቀልተዋል፡፡
ምነው ደህና አይደል ይሆን ? ያለቀሰ ይመስላል፡፡ የሞተ ሰው ይኖር ይሆን ? ያሬድም ደስተኛ አይመስልም፡፡ ዛሬ ምን ተፈጥሮ ይሆን ? አበበች ከውስጧ ሳታወጣና ሳታሰማ የተናገረችው ነበር፡፡
ምን ብሎ እንደሚነግራት ግራ ተጋብቷል፡፡ የቤቱን ጣራ ጣራ እየተመለከተ እንባው በጉንጩ ላይ ይወርዳሉ፡፡ አንገቱን ዞር አድርጎ ለመጥረግ ሞክረ፡፡
አበበች ግን ገና ሲገባ አንስታ እየተመለከተችው ነበር፡፡
"ምነው ደህና አይደለህም እንዴ? የምታለቅሰው" አለች ፤ ለተመስገን፡፡ የተፈጠረውን ለመስማት እየተጨናነቀች፡፡
ተመስገን ከተቀመጠበት ብርጩማ ላይ ተነስቶ ምንም በማታውቀው እና ምንም ባልሰማችው አበበች እግር ላይ ተደፋ፡፡ እባክሽን ከጉድ አውጭኝ ፤ በምትወጅው ልጅሽ ፤ በምትኩ ስም እለምንሻለሁ እያለ ያለቅስ ጀመር፡፡
አበበች ተመስገን ስለምን እንደሆነ የሚያወራው ግራ ተጋብታለች፡፡ ሲለምናትና ሲማፀናት ገና ባልሰማችውና ባላወቀችው ቀላል ነገር መስሏት እሽ፡፡አሁን ተነስ ብላ ካስነሳችው በኋላ፤ ምንድ ነው እሱ የቸገረህ"? አለችው፡፡ ተነስቶ ወደ ነበረበት የብሩጩማ ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡ አሁንም ከየት መጀመር እንዳለበት ግራ ቢገባውም መንፈሱ ብትጨነቅም ሚስጥሩን ለአበበች ካላካፈለ መፍትሄ ስለማያገኝ ደፍሮ መናገርና መተንፈስ አለበት፡፡ ራሱን አፅናንቶ ለመናገር ወሰነ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
የማን ይሁን ?
የባሰ! እሾክና መርፌ ተነቅሎ የማይጣል፤ በቅርብ ሳይገፋ ያልተደረሰበት ፤ ከላይኛው የወረደ ዱብዳ ፤ የፈጣሪ የቁጣ ስጦታ፡፡ ለማን ታድርገው? ለማን ትስጠው? ለማንስ አቤት ትበል? ተቆርጦ የማይጣል የጣት ቁስል ሆነባት፡፡
ቀኑ ወደ ጨለማ ተቀየረ፡፡ እንደ ተዳፈነ እሳት ውስጧን አቃጠለው፡፡ እንደ ሰኔ ደመና አረምሞ ገፍቷል፡፡ በአንድ ቀን ስህተት የእግዚአብሔር ስራ እንኳን ባይባልም በመቅሰፍቱ በዲያቢሎስ ቅንብር ሆዷ ውፍረትን መከታ እና ከለላ ተጠቅሞ ሳይታወቃት እየገፋ መጥቷል፡፡
እድላዊት ከወንድሟ ከተመስገን ፀንሳለች፡፡ በአንድ እንዴት ላረግዝ እችላለሁ?፡፡ ስታዝን ስትጨነቅ ዘጠኝ ወር ተቆጥሮ ቦርጩ ወደ ልጅ ተቀየረ፡፡ ወንድ ልጅ ከነ ቃጭሉ ተገላገለች፡፡ ግን ከፊቷ አሁንም የማይገፋ ከዳቢሎስ የተገነባ የጨለማ ተራራ ተጋርዶባታል፡፡
ምንጃር ሸንኮራ አውራጃ ውስጥ ነው፡፡ ጉራንባ ማርያም አካባቢ ያለ ማህበረሰብ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ናቸው፡፡ በእምነታቸው አክራሪና ከእምነት ውጭ ለሚከሰቱ ማንኛውም የክርስትና ጥፋት የፈፀመ ከማህበረሰቡ ይገለላል፡፡ እንደ እድር ፣ ባልትና እና ማህበር የመሳሰሉትን መካፈል አይችልም፡፡ በማህበረሱቡ የተጠላ ፤የማይወደድ ፣ ከሰው እንዳልተፈጠረ ከሰው ውጭ ተደርጎ ይቆጠራል።
እድላዊት እያወቀች ሳይሆን ሳታውቅ ከወንድሟ ከተመስገን መውለዷን ከያሬድ ውጭ ማንም አያውቅም፡፡
የወለደችውን ልጅ ክርስትና የሚነሳው የወላጅ አባት ስም ካልታወቀ መነሳት ፤ መጠመቅ የተወገዘና የተከለከለ ነው፡፡ የእድላዊት ልጅ ባለማወቅ አባት ታዲያ ማን ይሁን ? የማንስ ተብሎ ክርስትና ይጠመቅ ? አክ ተብሎ የተተፋ ምራቅ ተመልሶ አይዋጥ፡፡ የተመስገን ብትለው ለእሷ አንዴ ሞት ቢሆንም ለዘመዶቿና ለቤተሰቦቿ አስሬ ሞት ብቻ
ሳይሆን ከሰው እንዳልተፈጠሩና ወግ አጥባቂ የክርስትና አገልጋይ እንዳልሆኑ ከሰው ውጭ ተደርገው እንደሚገለሉ የሚታወቅ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡
ታዲያ እድላዊት ይህ ሁሉ የታዘለባትን የጭንቀት እሳት ማማከር ያለባት ለወንድሟ ለተመስገን እንጅ ለማንም ማማከር እንደ ማይቻል ግልፅ ነው፡፡ ግን አሁንም ሌሊቱ ጨልሞባታል፡፡
"ምን እናድርግ ? የልጁ የክርስትና ቀን እየደረሰ ነው፡፡ እኔ ጨንቆኛል፡፡ የማደርገው ጠፍቶኛል፡፡ ከእንግዴህ ያለኝ አማራጭ መርዝ ጠጥቸ ወይም ታንቄ መሞት ነው፡፡ የወንድሜ ነው ብየ ክርስትና አላስነሳም፡፡ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡
ተመስገን የእህቱ ጭንቀት በሱም ላይ ካደረበት እና ከሰነበተበት ቆይቷል፡፡ ጥሎ እንዳይጠፋ እድላዊትን ተመልሶ ዳግመኛ የማያገኛት መሰለው፡፡
እድላዊት እያለቀሰች መልስ እንኳን ሳይሰጣት ከያሬድ ጋር ደርሸ መጣሁ ብሏት ተነስቶ ወደ ያሬድ ቤት ሄደ፡፡
ተመስገን እንደደረሰ ከያሬድ ጋር የእግዚአብሔር ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ ያሬድ ወደ እርሻ ሊሄድ ሞፈርና ቀንበር እያዘጋጀ ነው፡፡
"ወደ እርሻ ልትሄድ ነው እንዴ ሞፈርና ቀንበር የምታሰናዳው?" አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አዎ፤ እንዴው ትንሽ የፋልማ መሬት ከሰም ነበረኝ፡፡ ቧጠጥ አድርጌያት ልምጣ ብዬ ነበር አነሳሴ፡፡ ስተረካከም እዚሁ እረፈደ ብሎ ወደ ቤት ግባ እንጅ አለው፡፡
"ኧረ አልገባም፡፡ አንተ ጋር ነበር የመጣሁት"፡፡
"ምነው በደህና ነው"? አለ ፤ ያሬድ፡፡
"ምን ደህንነት አለ ፤ ገና ስፈጠር የአርባ ቀን እድሌ በእሳት ተሞልቶ የእሳት እረመጡ ወደ ጭስነት ተቀይሮ የመውጭያ በር አጥቶ በቁሜ እያቃጠለኝ፡፡
"ምነው እድላዊት ሰላም አይደለችም እንዴ?፡፡
"አይ! ተወኝ ፤ አሁን የእድላዊት ነገር አስጨንቆኛል፡፡ የልጁ ክርስትና እየደረሰ ነው፡፡ የአባቱ ስም ካልታወቀ ክርስትና እንደ ማይጠመቅ አንተም ታውቃለህ፡፡
የማደርገው ሁሉ ግራ ገብቶኛል፡፡ ወንድሜ እባክህ ከዚህ ጨለማ አውጣኝ፡፡ ያላንተ ማንም የማዋየውና የማማክረው የለኝም አለው፡፡በሃዘን ተሞልቶ ፡፡
"በምን ልርዳህ የማደርገው ጠፍቶኝ እኮ ነው፡፡ እስከ አሁንም ዝም ያልኩህ እንጅ እኔ እንኳን ወደ አዲስ አበባ ይዘናት እንድንሄድ አስቤ ነበር፡፡ ግን ክርስትና ሳታስነሳ ከቤት መውጣት አይቻልም ብየ ነው፡፡ አሁን በምን ላግዛችሁ ? ንገረኝና በተቻለኝ አቅም ልሞክር አለ፡፡
በፊቱ ላይ ወርዶ ቡሃቃ ያስመሰለውን እንባ በለበሰው ፎጣ እየጠራረገ እኔማ ለመጥፋትም አስቤ ነበር፡፡ ግን እድላዊት ጥሎ የሚሄድ አንጄት አጣሁ፡፡ አሁን አንተን የማስቸግርህ ልጁ ክርስትና እስከሚነሳ ድረስ የአባቱን ስም በአንተ እናድርግና ክርስትና ከተጠመቀ በኋላ ፤ የተፈጠረውንና የተደረገውን ባለመተዋወቅ እንደ ሆነ ለቤተሰብ እንነግራለን አለ፤ ተመስገን ፡፡ ደፍሮ በመናገሩ አይኑን ላለማየት አቀርቅሮ መሬት መሬት እያየ፡፡
የልጁ አባት ሆኘ ክርስትና ቢጠመቅ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን የአካባቢያችንን ባህል እንደምታውቀው በሚስቱ ላይ ዲቃላ ወልዷል ተብየ እኔ ከማህበረሰብ እንደምገለል፡፡ ደግሞም ባለቤቴ ይህንን ስሰማ በእኔ ላይ ዲቃላህን ታንጠባጥባለህ ብላ ባዶቤት ዘግታብኝ ትሄዳለች አለ ፤ ያሬድ፡፡
"ያልከው ሁሉም ይገባኛል፡፡ ግን ከወንድሟ ወለደች ቢባል ምን ያህል እንደሚከብድ መገመት አያቅትህም፡፡ ደግሞ አባታችን በዚህ ቦታ ወግ አጥባቂ እንደ ሆነ ታውቃለህ፡፡
እባክህ! ያሬድ ስለፈጠረህ አምላክ! ተለመነኝ ሳላውቅ እንደ ሆነ እሳት ውስጥ የገባሁት አንተም ታውቃለህ፡፡ ሚስጥሩን ለባለቤትህ እንነግራታለን፡፡ መጀመሪያ አንተ ብቻ እሽ በለኝ፡፡ እያለቀሰ ተማፀነው፡፡
ያሬድ የሚለው ሁሉ ጨነቀው፡፡ የእድላዊትና የተመስገን ስቃና መከራ የሱም ሆነ፡፡ ክርስትናው እስከሚያልፍ የልጁ አባት ለመሆን ብቻውን መወሰን አልቻለም፡፡
"ለማንኛውም አበበችን አብረን ሚስጥሩን እናካፍላትና እሷ እሽ ካለች የእኔ አያስቸግርም፡፡ አይቻልም ካለች ግን ምንም ላደርግ አልችልም" አለው
"እሽ አንተ እንዳልክ" ብሎት ወደ ቤት ገቡ፡፡
"ደህና አደርሽ አበበች" ? አለ ፤ ተመስገን፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደርክ ተመስገን" ? አለች ፤ አበበች፡፡
ጉንጮቹ አብጠው ገና በጥዋቱ አይኖቹ ቀልተዋል፡፡
ምነው ደህና አይደል ይሆን ? ያለቀሰ ይመስላል፡፡ የሞተ ሰው ይኖር ይሆን ? ያሬድም ደስተኛ አይመስልም፡፡ ዛሬ ምን ተፈጥሮ ይሆን ? አበበች ከውስጧ ሳታወጣና ሳታሰማ የተናገረችው ነበር፡፡
ምን ብሎ እንደሚነግራት ግራ ተጋብቷል፡፡ የቤቱን ጣራ ጣራ እየተመለከተ እንባው በጉንጩ ላይ ይወርዳሉ፡፡ አንገቱን ዞር አድርጎ ለመጥረግ ሞክረ፡፡
አበበች ግን ገና ሲገባ አንስታ እየተመለከተችው ነበር፡፡
"ምነው ደህና አይደለህም እንዴ? የምታለቅሰው" አለች ፤ ለተመስገን፡፡ የተፈጠረውን ለመስማት እየተጨናነቀች፡፡
ተመስገን ከተቀመጠበት ብርጩማ ላይ ተነስቶ ምንም በማታውቀው እና ምንም ባልሰማችው አበበች እግር ላይ ተደፋ፡፡ እባክሽን ከጉድ አውጭኝ ፤ በምትወጅው ልጅሽ ፤ በምትኩ ስም እለምንሻለሁ እያለ ያለቅስ ጀመር፡፡
አበበች ተመስገን ስለምን እንደሆነ የሚያወራው ግራ ተጋብታለች፡፡ ሲለምናትና ሲማፀናት ገና ባልሰማችውና ባላወቀችው ቀላል ነገር መስሏት እሽ፡፡አሁን ተነስ ብላ ካስነሳችው በኋላ፤ ምንድ ነው እሱ የቸገረህ"? አለችው፡፡ ተነስቶ ወደ ነበረበት የብሩጩማ ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡ አሁንም ከየት መጀመር እንዳለበት ግራ ቢገባውም መንፈሱ ብትጨነቅም ሚስጥሩን ለአበበች ካላካፈለ መፍትሄ ስለማያገኝ ደፍሮ መናገርና መተንፈስ አለበት፡፡ ራሱን አፅናንቶ ለመናገር ወሰነ፡፡
👍52❤4
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አይንሽን ላፈር
አይ! ሰው ለሰው ሞት አነሰው ብላ የተረተችው ቀበሮ ወዳም አይደለም፡፡ ለካ ለሁሉም የሚተረትለት ችግሩ በቤቱ ሲደርስበት ኖሯል፡፡ ለነሱ ብዬ ስሜ በማንም አፈኛ በየገብያውና በየቤቱ ይነሳል፡፡ እቤት ተዘፍዝፋ ባሏ ዲቃላ ያንጠባጥባል፡፡ ምን አይነት ግፍንት ነች እየተባልኩ የማንም መሳቂያና መተረቻ ልሁን? ከሰውም ጋር ባይሆንም ከራሷ ሃሳብ ጋር ያወራችው ነበር ፡፡
ስሙን ሳነሳሳና ሳማው መጣ እንዴ? ከውጭ በኩል አበበች የሚል የወንድ ድምፅ ሰምታ ተመስገን መስሏት ነበር፡፡ ከተቀመጠችበት ተነስታ ወጣች፡፡
ግን ተመስገን ሳይሆን ወላጅ አባቷ አቶ አሸናፊ ነበር፡፡
"ደህና አረፈዳችሁ"? አለ ፤ አቶ አሸናፊ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አረፈድህ አባባ ፤ ግባ ወደ ቤት" አለች፡፡
ወደ እቤት እየገቡ "ያሬድ የለም እንዴ"? አለ፡፡
"የለም፤ በጥዋት መጣሁ ብሎኝ እንደ ሄደ አልተመለሰም፡፡ የሄደበትንም አልነገረኝም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም?፡፡
"እኔስ ደህናነኝ፡፡ ከብቶቹ እፀሃይ ላይ ታስረው ሳይ ለምን አልፈታቸውም ብዬ ነው"፡፡
"እኔም ብዬ አሁን ነበር የሚበላ የሰጠኋቸው፡፡ ውሃ ጠምቷቸው ነው መሰለኝ አልበሉትም፡፡ እሱም ውሃ እንዳያጠጣቸው ብቅታውም ጠፋ፡፡ ወይ እቆያለሁ አጠጫቸው እንኳን አላለኝ፡፡ ቶሎ እንደሚመለስ ሰው ሳይነግረኝ መሔዱ አለች፡፡
"መቼ ጉዳይ ብሎ ነው፡፡ ከብት አጠጥቶ የሚያውቀው፡፡ አንዴ ነጋዴ ነኝ ፤ አንዴ ባለጉዳይ ነኝ
እያለ ፤ መንደር ለመንደርና ከተማ ለከተማ እያሽካካና እየዞረ አላት፡፡
"እንዴው እቤት ካለ ብዬ ነው እንጂ ለማጠጣቱማ አዲስ አይደለሁም፡፡ አሁን ለአንተ ቡና ላፍላና አጠጣቸዋለሁ፡፡
"እኔ ቡና አልጠጣም፡፡ አታፍሊ ፡፡
"ለምን አትጠጣም? ምነው ደህና አይደለህም? እንዴ አለችው፡፡ አባቷ ተኮሳትሮ መናገሩ አስፈርቷታል፡፡
አቶ አሸናፊ በሚወራው የሰፈር ወሬ ማንነቱን ያስደፈረው ይመስላል፡፡ ወደ ልጁ ቤት የመጣው እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ ለበጎ ሳይሆን ለነገር እንደመጣ በፊቱ ላይ የሚነበበው የመኮሳተር ምልክት የሚያስይ መሆኑ ጥርጥር የለውም ነበር፡፡
"አንቺ ወራዳ ፤ አንቺ ተዋርደሽ እኔንም አዋረድሽኝ፡፡ ባልሽ አንቺን የቤት ገረድ አድርጎ ዲቃላውን በሔደበት ይፈለፍላል፡፡ ከሰማሽ በኋላ፤ እንኳን ጥለሽ መምጣት አቅቶሽ ነው" አለ፡፡ በዱላ እንደ መምታት ያህል በሚሰማ ንግግር፡፡
አበበች የፈራችው አልቀረም፡፡ በትዳሯ ላይ እሳት ሲለኮስ ታያት፡፡ የአባቷ ንግግር ከያሬድ ጋር እንድትቀጥል የሚፈልግ አይመስልም፡፡ ለተመስገን እሽ ያለችበትን ቀን አምርራ ብትረግምም ያቺን ቀን ግን ተመልሳ ልታገኛት አልቻለችም፡፡ መልስ ሳትሰጥ አይኞቿ በእንባ ተሞሉ፡፡
"አሁን ምንድ ነው ሃሳብሽ ? የባልሽ ገረድ ሆኖ መቀጠል ይሻላል?፡፡ ወይስ ለቆ መውጣት ይሻላል?፡፡ መነፋረቁን ትተሸ ተናገሪ አለ፡፡ አሁንም ቁጣና ንዴት በተቀላቀለበት ንግግር፡፡
"አባባ የማታውቀው ነገር ስላለ እኮ ነው ብላ..
"የማላውቀው ምንድ ነው ባክሽ?፡፡ ከቄስ መልካሙ ልጅ ባልሽ መውለዱን ነው፤ የማላቀው? ወይስ በማንም ጨምላቃ አፍ በየቡና ቤቱ ላይ በአንች የተነሳ ስሜ መነሳቱን ነው የማላውቀው?፡፡ ለነገሩ እኔ የተዋረድኩት ዛሬ ሳይሆን አንቺን የወለድሁ ቀን ነው አላት፡፡
ሚስጥሩን ለአባቷ ለመንገር ብትፈልግም አባቷ ግን ምንም አይነት ምክንያት የሚቀበል አይደለም፡፡
"ትዳሬን እንዴት ባልሰራሁት ለቅቄ እሄዳለሁ?
ልጄን ያለ አባት ማሳደግ አልፈልግም፡፡ ነገ እውነቱ ሲወጣ ጥፋተኛ ማን እንደሆነ ያኔ ታውቃለህ አለች፡፡ ደፍራ በመናገሯ አይኑን ላለማየት ወደ መሬት አቀርቅራ፡፡
አቶ አሸናፊ የባሰ በንዴት ቆሽታቸው አረረ፡፡ አንች ወራዳ አታፍሪም ደግሞ ነገ እውነቱ ይወጣል ስትይኝ?፡፡ አንገታቸውን እየነቀነቁ አይ! አለመታደል ይሄ! ልክስክስ ባልሽ ካዋጣሽ ከዛሬ ጀምሮ! ልጄ! አይደለሽም፡፡ ብሞትም እንኳን ከመቃብሬ ላይ እንዳትቆሚ፡፡ ብሏት፤ የወለዳትን ልጅ ረግሞ እንዳልወለዳት ልጄ አይደለሽም ብሎ እያለቀሰች ትቷት ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ታዲያ አበበች ስታለቅስ አይን አይኗን እያዬ የሚቁለጨለጨው ልጇ ለተመለከተው ከሷ ለቅሶ ይልቅ የልጇ አይኖች ሲንከራተቱ ያስለቅሱ ነበር፡፡
"ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው"? አለ ፤ ያሬድ፡፡ ባለቤቱን ጥዋት ትቷት ሲወጣ ደህና ብትሆንም ሲመለስ ግን እያለቀሰች ስላገኛት፡፡ በምን እንደምታለቅስ ግራ ገባው፡፡ ልጁን ከእቅፏ ላይ አንስቶ ታቀፈው፡፡ ባየው ነገር ሆዱ ባባ፡፡ ከየት መጣ ሳይባል እንባ ከአይኖቹ ተንጠባጠቡ፡፡
የተፈጠረውን ለማውቅ ደግሞ "ምንድ ነው የሆሽው? ለምን አትነግሪኝም? አለ ፤ እንደ መቆጣት ብሎ፡፡
አበበች እንባዋን እየጠራረገች አባባ አሁን መጥቶ ነበር አለች፡፡
"ታዲያ ምን አሉሽ ?፡፡
"ምን ይለኛል፡፡ ያው እየፈራን ላደረግነው ነገር አይንሽን ለአፈር አለኝ፡፡ አንቺ የባልሽ ገረድ ሆነሽ ባልሽ ዲቃላውን ይፈለፍላል፡፡ አሁን ባሌ ይሻለኛል ካልሽ ከዛሬ ጀምሮ ልጄ አይደለሽም፡፡ ብሞት እንኳን ከመቃብሬ ላይ እንዳትቆሚ ብሎኝ እያለቀስኩ አሁን ነው ጥሎኝ የወጣው፡፡
"ሚስጥሩን ነገርሻቸው እንዴ"?፡፡
"እኔ ልነግረው አስቤ ነበር፡፡ እሱ ግን የሚሰማኝ ስላልመሰለኝ አልነገርኩትም፡፡
"ድሮም እግዚአብሔርን ብለን እንጅ ይሄ እንደሚመጣ እያወቅን የገባንበት ነው፡፡ አሁን እውነቱ
እስከሚወጣ ድረስ የምናደርገው ምንም አይኖርም፡፡
ሚስጥሩ መውጣት ያለበት የእነሱም ቤተሰቦች የእኛም ቤተሰቦች ተሰብስበው ነው፡፡ እኔም ትላንትና አልነገርኩሽም እንጅ ከገበያ ስመጣ ወንድምሽ ከመንገድ አድፍጦ ሊገለኝ ሲል እሮጨ ነው ያመለጥኩት፡፡ ሁሉም ነገር ጥፋቱ የእኔ እስከሆነ ድረስ በእነሱ የምይዝባቸው ቂም የለኝም፡፡ ከአሁን በኋላ፤ እናትሽም ቢመጡም ሚስጥሩን እንዳትነግሪ፡፡ ምክንያቱም ወሬው በውጭ ከተወራ ተመስገንና እድላዊት ራሳቸውን ሊያጠፉ ይችላሉ፡፡ እነሱ ከሌሉ ሁሉም ነገር ጨለማ ለብሶ ሳይገለጥ ተዳፍኖ እንዳይቀር ጥንቃቄ ያስፈልገናል፡፡
ወዶዘማች
ወደ ጠጁ ቤቱ ጎራ አለ፡፡ አንድ ብርሌ ጠጅ አዘዘ፡፡ ሁለት አውቶቢስ አንድ ሚኒባስ ከላይዋ ላይ ድምፅ ማጉሊያ ጭና ከፊት ለፊት ቀድማ ትከንፋለች፡፡ የአስረስ ሽለላና ቀረርቶ በከፍተኛ ድምፅ ተለቋል፡፡ የአረርቲ ከተማን ከዳር እስከ ዳርም አናውጧታል፡፡ ታዲያ ሽለላና ቀረርቶው በጥቂቱ እንዲህ ይል ነበር፡፡
ኧረ ጎራው ኧረ መርዙ፤
ኧረ ጎራው ኧረ መርዙ፤
እንኳን በለው ብለው ልከው ሰደውት፤
ከወገብ ላይ ሆኖ ያኮራል ጥይት፡፡
ኧረ ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ከአፈሙዙ ዘቅዘቅ ከሰደፉ ቀና አድርገው የተኮሱ እንደሆን፤
ጥይት ሰው አይፈራም ምን ደንደሳም ቢሆን፡፡
ኧረ ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ዘሩ የመርዙ ትውልድ፤
አምሶ ይቀብራል እንደ እሳት ሰደድ፤
ኧረ ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ሀገሬ ኢትዮጵያ ኩሪ ይገባሻል፤
የማያስደፍሩ ጀግና ልጅ ወልደሻል፡፡
ኧረ ጎራው ኧረ መርዙ፤
አገሬን ኢትዮጵያ እሳት ይዞረዋል፤
ለመጥፋት ነው እንጅ ምን ይሻገረዋል፡፡
ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ዘራፍ የተጎረፈው በጠመንጃው ፊት ሰው የማያልፈው፤ ሳይነካኳቸው እየደረሱ ይመለሳሉ እየቀመሱ ፤
ታንክ ቢያሽካካ መድፍ ቢያጓራ፤
የሚጋፈጠው በሮ እንደ አሞራ፡፡….
ከአስረስ ሽለላና ቀረርቶ በተጨማሪ ጋዜጠኛ ገረመው ይታያል እሱም እንዲህ ይል ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አይንሽን ላፈር
አይ! ሰው ለሰው ሞት አነሰው ብላ የተረተችው ቀበሮ ወዳም አይደለም፡፡ ለካ ለሁሉም የሚተረትለት ችግሩ በቤቱ ሲደርስበት ኖሯል፡፡ ለነሱ ብዬ ስሜ በማንም አፈኛ በየገብያውና በየቤቱ ይነሳል፡፡ እቤት ተዘፍዝፋ ባሏ ዲቃላ ያንጠባጥባል፡፡ ምን አይነት ግፍንት ነች እየተባልኩ የማንም መሳቂያና መተረቻ ልሁን? ከሰውም ጋር ባይሆንም ከራሷ ሃሳብ ጋር ያወራችው ነበር ፡፡
ስሙን ሳነሳሳና ሳማው መጣ እንዴ? ከውጭ በኩል አበበች የሚል የወንድ ድምፅ ሰምታ ተመስገን መስሏት ነበር፡፡ ከተቀመጠችበት ተነስታ ወጣች፡፡
ግን ተመስገን ሳይሆን ወላጅ አባቷ አቶ አሸናፊ ነበር፡፡
"ደህና አረፈዳችሁ"? አለ ፤ አቶ አሸናፊ፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አረፈድህ አባባ ፤ ግባ ወደ ቤት" አለች፡፡
ወደ እቤት እየገቡ "ያሬድ የለም እንዴ"? አለ፡፡
"የለም፤ በጥዋት መጣሁ ብሎኝ እንደ ሄደ አልተመለሰም፡፡ የሄደበትንም አልነገረኝም፡፡ ምነው ደህና አይደለህም?፡፡
"እኔስ ደህናነኝ፡፡ ከብቶቹ እፀሃይ ላይ ታስረው ሳይ ለምን አልፈታቸውም ብዬ ነው"፡፡
"እኔም ብዬ አሁን ነበር የሚበላ የሰጠኋቸው፡፡ ውሃ ጠምቷቸው ነው መሰለኝ አልበሉትም፡፡ እሱም ውሃ እንዳያጠጣቸው ብቅታውም ጠፋ፡፡ ወይ እቆያለሁ አጠጫቸው እንኳን አላለኝ፡፡ ቶሎ እንደሚመለስ ሰው ሳይነግረኝ መሔዱ አለች፡፡
"መቼ ጉዳይ ብሎ ነው፡፡ ከብት አጠጥቶ የሚያውቀው፡፡ አንዴ ነጋዴ ነኝ ፤ አንዴ ባለጉዳይ ነኝ
እያለ ፤ መንደር ለመንደርና ከተማ ለከተማ እያሽካካና እየዞረ አላት፡፡
"እንዴው እቤት ካለ ብዬ ነው እንጂ ለማጠጣቱማ አዲስ አይደለሁም፡፡ አሁን ለአንተ ቡና ላፍላና አጠጣቸዋለሁ፡፡
"እኔ ቡና አልጠጣም፡፡ አታፍሊ ፡፡
"ለምን አትጠጣም? ምነው ደህና አይደለህም? እንዴ አለችው፡፡ አባቷ ተኮሳትሮ መናገሩ አስፈርቷታል፡፡
አቶ አሸናፊ በሚወራው የሰፈር ወሬ ማንነቱን ያስደፈረው ይመስላል፡፡ ወደ ልጁ ቤት የመጣው እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ ለበጎ ሳይሆን ለነገር እንደመጣ በፊቱ ላይ የሚነበበው የመኮሳተር ምልክት የሚያስይ መሆኑ ጥርጥር የለውም ነበር፡፡
"አንቺ ወራዳ ፤ አንቺ ተዋርደሽ እኔንም አዋረድሽኝ፡፡ ባልሽ አንቺን የቤት ገረድ አድርጎ ዲቃላውን በሔደበት ይፈለፍላል፡፡ ከሰማሽ በኋላ፤ እንኳን ጥለሽ መምጣት አቅቶሽ ነው" አለ፡፡ በዱላ እንደ መምታት ያህል በሚሰማ ንግግር፡፡
አበበች የፈራችው አልቀረም፡፡ በትዳሯ ላይ እሳት ሲለኮስ ታያት፡፡ የአባቷ ንግግር ከያሬድ ጋር እንድትቀጥል የሚፈልግ አይመስልም፡፡ ለተመስገን እሽ ያለችበትን ቀን አምርራ ብትረግምም ያቺን ቀን ግን ተመልሳ ልታገኛት አልቻለችም፡፡ መልስ ሳትሰጥ አይኞቿ በእንባ ተሞሉ፡፡
"አሁን ምንድ ነው ሃሳብሽ ? የባልሽ ገረድ ሆኖ መቀጠል ይሻላል?፡፡ ወይስ ለቆ መውጣት ይሻላል?፡፡ መነፋረቁን ትተሸ ተናገሪ አለ፡፡ አሁንም ቁጣና ንዴት በተቀላቀለበት ንግግር፡፡
"አባባ የማታውቀው ነገር ስላለ እኮ ነው ብላ..
"የማላውቀው ምንድ ነው ባክሽ?፡፡ ከቄስ መልካሙ ልጅ ባልሽ መውለዱን ነው፤ የማላቀው? ወይስ በማንም ጨምላቃ አፍ በየቡና ቤቱ ላይ በአንች የተነሳ ስሜ መነሳቱን ነው የማላውቀው?፡፡ ለነገሩ እኔ የተዋረድኩት ዛሬ ሳይሆን አንቺን የወለድሁ ቀን ነው አላት፡፡
ሚስጥሩን ለአባቷ ለመንገር ብትፈልግም አባቷ ግን ምንም አይነት ምክንያት የሚቀበል አይደለም፡፡
"ትዳሬን እንዴት ባልሰራሁት ለቅቄ እሄዳለሁ?
ልጄን ያለ አባት ማሳደግ አልፈልግም፡፡ ነገ እውነቱ ሲወጣ ጥፋተኛ ማን እንደሆነ ያኔ ታውቃለህ አለች፡፡ ደፍራ በመናገሯ አይኑን ላለማየት ወደ መሬት አቀርቅራ፡፡
አቶ አሸናፊ የባሰ በንዴት ቆሽታቸው አረረ፡፡ አንች ወራዳ አታፍሪም ደግሞ ነገ እውነቱ ይወጣል ስትይኝ?፡፡ አንገታቸውን እየነቀነቁ አይ! አለመታደል ይሄ! ልክስክስ ባልሽ ካዋጣሽ ከዛሬ ጀምሮ! ልጄ! አይደለሽም፡፡ ብሞትም እንኳን ከመቃብሬ ላይ እንዳትቆሚ፡፡ ብሏት፤ የወለዳትን ልጅ ረግሞ እንዳልወለዳት ልጄ አይደለሽም ብሎ እያለቀሰች ትቷት ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ታዲያ አበበች ስታለቅስ አይን አይኗን እያዬ የሚቁለጨለጨው ልጇ ለተመለከተው ከሷ ለቅሶ ይልቅ የልጇ አይኖች ሲንከራተቱ ያስለቅሱ ነበር፡፡
"ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሽው"? አለ ፤ ያሬድ፡፡ ባለቤቱን ጥዋት ትቷት ሲወጣ ደህና ብትሆንም ሲመለስ ግን እያለቀሰች ስላገኛት፡፡ በምን እንደምታለቅስ ግራ ገባው፡፡ ልጁን ከእቅፏ ላይ አንስቶ ታቀፈው፡፡ ባየው ነገር ሆዱ ባባ፡፡ ከየት መጣ ሳይባል እንባ ከአይኖቹ ተንጠባጠቡ፡፡
የተፈጠረውን ለማውቅ ደግሞ "ምንድ ነው የሆሽው? ለምን አትነግሪኝም? አለ ፤ እንደ መቆጣት ብሎ፡፡
አበበች እንባዋን እየጠራረገች አባባ አሁን መጥቶ ነበር አለች፡፡
"ታዲያ ምን አሉሽ ?፡፡
"ምን ይለኛል፡፡ ያው እየፈራን ላደረግነው ነገር አይንሽን ለአፈር አለኝ፡፡ አንቺ የባልሽ ገረድ ሆነሽ ባልሽ ዲቃላውን ይፈለፍላል፡፡ አሁን ባሌ ይሻለኛል ካልሽ ከዛሬ ጀምሮ ልጄ አይደለሽም፡፡ ብሞት እንኳን ከመቃብሬ ላይ እንዳትቆሚ ብሎኝ እያለቀስኩ አሁን ነው ጥሎኝ የወጣው፡፡
"ሚስጥሩን ነገርሻቸው እንዴ"?፡፡
"እኔ ልነግረው አስቤ ነበር፡፡ እሱ ግን የሚሰማኝ ስላልመሰለኝ አልነገርኩትም፡፡
"ድሮም እግዚአብሔርን ብለን እንጅ ይሄ እንደሚመጣ እያወቅን የገባንበት ነው፡፡ አሁን እውነቱ
እስከሚወጣ ድረስ የምናደርገው ምንም አይኖርም፡፡
ሚስጥሩ መውጣት ያለበት የእነሱም ቤተሰቦች የእኛም ቤተሰቦች ተሰብስበው ነው፡፡ እኔም ትላንትና አልነገርኩሽም እንጅ ከገበያ ስመጣ ወንድምሽ ከመንገድ አድፍጦ ሊገለኝ ሲል እሮጨ ነው ያመለጥኩት፡፡ ሁሉም ነገር ጥፋቱ የእኔ እስከሆነ ድረስ በእነሱ የምይዝባቸው ቂም የለኝም፡፡ ከአሁን በኋላ፤ እናትሽም ቢመጡም ሚስጥሩን እንዳትነግሪ፡፡ ምክንያቱም ወሬው በውጭ ከተወራ ተመስገንና እድላዊት ራሳቸውን ሊያጠፉ ይችላሉ፡፡ እነሱ ከሌሉ ሁሉም ነገር ጨለማ ለብሶ ሳይገለጥ ተዳፍኖ እንዳይቀር ጥንቃቄ ያስፈልገናል፡፡
ወዶዘማች
ወደ ጠጁ ቤቱ ጎራ አለ፡፡ አንድ ብርሌ ጠጅ አዘዘ፡፡ ሁለት አውቶቢስ አንድ ሚኒባስ ከላይዋ ላይ ድምፅ ማጉሊያ ጭና ከፊት ለፊት ቀድማ ትከንፋለች፡፡ የአስረስ ሽለላና ቀረርቶ በከፍተኛ ድምፅ ተለቋል፡፡ የአረርቲ ከተማን ከዳር እስከ ዳርም አናውጧታል፡፡ ታዲያ ሽለላና ቀረርቶው በጥቂቱ እንዲህ ይል ነበር፡፡
ኧረ ጎራው ኧረ መርዙ፤
ኧረ ጎራው ኧረ መርዙ፤
እንኳን በለው ብለው ልከው ሰደውት፤
ከወገብ ላይ ሆኖ ያኮራል ጥይት፡፡
ኧረ ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ከአፈሙዙ ዘቅዘቅ ከሰደፉ ቀና አድርገው የተኮሱ እንደሆን፤
ጥይት ሰው አይፈራም ምን ደንደሳም ቢሆን፡፡
ኧረ ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ዘሩ የመርዙ ትውልድ፤
አምሶ ይቀብራል እንደ እሳት ሰደድ፤
ኧረ ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ሀገሬ ኢትዮጵያ ኩሪ ይገባሻል፤
የማያስደፍሩ ጀግና ልጅ ወልደሻል፡፡
ኧረ ጎራው ኧረ መርዙ፤
አገሬን ኢትዮጵያ እሳት ይዞረዋል፤
ለመጥፋት ነው እንጅ ምን ይሻገረዋል፡፡
ገዳይ ኧረ ገዳይ፤
ዘራፍ የተጎረፈው በጠመንጃው ፊት ሰው የማያልፈው፤ ሳይነካኳቸው እየደረሱ ይመለሳሉ እየቀመሱ ፤
ታንክ ቢያሽካካ መድፍ ቢያጓራ፤
የሚጋፈጠው በሮ እንደ አሞራ፡፡….
ከአስረስ ሽለላና ቀረርቶ በተጨማሪ ጋዜጠኛ ገረመው ይታያል እሱም እንዲህ ይል ነበር፡፡
👍52❤9
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
የገመሪ ተራራ
የተደበቀው ሚስጥር እንዳይወጣበት ከዛሬ ነገ እያለ እንደሌባ በሩቁ ይሸሻል፡፡ የሱ ጉዳዩ ከተፈፀመለት በኋላ፤ ተመልሶ ወደ ያሬድ ቤት አልሄደም፡፡ ጓደኛው ወደ ውትድርና መግባቱን ሲሰማ ስጋትና
ጭንቀት አላስቀመጠውም፡፡ የአበበችን ዓይን ማየት አልቻለም፡፡
ያለውን ንብረት እንዳይነቃበት በከፊል ሸጠ፡፡ ከእድላዊት ጋር ሃገር ለቀው ለመሄድ ተስማሙ፡፡ ለመንገድ የሚሆን በሶና ቆሎ አዘጋጁ፡፡ ስደትን መርጠዋል፡፡ ልጃቸውንና እናት አባታቸውን ያለጧሪ ፣ ቀባሪ ትተው ለመሄድ ተነሱ፡፡ አንጀታቸው አዘነ፡፡ አይናቸው አነባ፡፡ ልባቸው ግን ጨክኗል፡፡ ቤተሰቦቻቸውን ፀበል ነው የምንሄደው ብለው ዋሽተዋቸዋል፡፡ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት በዕለተ ሰንበት ሰው ወደ ቤተክርስትያን ለመሳም በሚሄድበት ሰዓት እነሱ ወደ አረብ ሃገር ስደት ሆነ፡፡ ከሰም ጅረቱን አቋርጠው በደብረብርሃን አድርገው ወደ ወሎ ባቲ ተጓዙ፡፡
ከሶስት ቀን ጎዞ በኋላ ባቲ ከተማ እንደደረሱ በቀይ ሸራ ወደ ተሸፈነች የሻይ ድንኳን ጎራ አሉ፡፡
በጦስኝ ቅመም የተንቆጠቆጠ የባቲ ሻይ አዘዙ፡፡
አንድ መልከ መልካም ወጣት ወደ ሻይ ቤቷ ገባ፡፡
"ቶሎ በል አንድ ሻይ በዳቦ ስጠኝ ? ሰዎች እየጠበቁኝ ነው አለ ፤ ወጣቱ እየተጣደፈ፡፡
የሻይ አስተናጋጁ "እነማን ናቸው የሚጠብቁህ"? አለ፡፡
ወደ አረብ ሃገር የሚሄዱ ናቸው፡፡ ከመሃመድ ጋር አገናኝቻቸው ልመጣ ነው አለ፡፡ ያዘዘውን ሻይና ዳቦውን ሲበላ ለተመለከተው የቸኮለ ሰው ሳይሆን ከጎሬ የወጣ ጅብ ይመስል ነበር፡፡
ወደ አረብ ሃገር በየት እንደሚኬድ አያውቁም፡፡
"ይሄንን ልጅ እንጠይቀው" ? አለች እድላዊት፡፡ ወጣቱ ስለ አረብ ሃገር ሲያወራ ሰምታ፡፡
ተመስገን ለመጠየቅ ፈራ ተባ አለ፡፡ ኧረ! ለመሄድ ተቻኩሏል ሳይነሳ ጠይቀው አለች ? ደግማ፡፡
"ወንድም" ? አለ ፤ ተመስገን፡፡ ከሻይና ከዳቦ ጋር እየታገለ ያለውን ወጣት፡፡
"አቤት ጠራኸኝ" ? አለ ፤ ወጣቱ፡፡
"አዎ፤ አንድ ነገር ትተባበረኛለህ ?፡፡
አላመነታም፡፡ "ምን ልተባበራችሁ? ወደ አረብ ሃገር መሄድ ትፈልጋላችሁ? ፡፡
"አዎ፤ ለመሄድ ፈልገን ነበር ፡፡
"እኔ ደላላ ነኝ፡፡ ከሚልከው ሰው ጋር እንዳገናኛችሁ፡፡ ከፈለጋችሁ ሁለታችሁም አርባ አርባ ብር ክፈሉኝ ብሎ ለመሄድ ተነሳ፡፡
"እሽ እንከፍልሃለን፡፡ ታዲያ አሁን የት ልትሄድ ነው? አለው፡፡
"ሰው እየጠበቀኝ ነው፡፡ ቼኩያዓለሁ ፤ ከሄዳችሁ ብሩን አምጡና ተነሱ እንሂድ አላቸው፡፡
"እሽ" አሉ፡፡ የያዙትን ገንዘብ ከፍለው ደላላውን ተከተሉት፡፡
ወደ ውጭ ሃገር የሚልኳቸውን የሰዎች ማሰባሰቢያ ቤት ደረሱ፡፡ መሃመድ ለሚባል ደላላ አስረክቧቸው ተመለሰ፡፡
መሃመድ ተቀብሎ ወደ ውጭ ሃገር ሊወስዳቸው ካሰባሰባቸው ስምንት ሴትና አስር ወንዶች ጋር ቀላቅሎ በራሱ መኪና አሳፍሮ አስኢት ከተማ አደረሳቸው፡፡
እሱም ለአስኢት ደንበኛው ለከድር አስረክቧቸው ተመለሰ፡፡
የአስኢት ደላላው ከድር ከመሃመድ ዘጠኝ ሴቶችንና አስራ አንድ ወንዶችን በድምሩ ሃያ ሰዎችን ተቀብሎ ከአስኢት ከተማ ጉዞ በምሽት ጫካ ለጫካ በእግር ወደ የቡኪ ተጀመረ፡፡
የቡኪ የኢትዮጵያ አፋር መሬትን ጨርሶ የጅቡቲ መዳረሻ መሬት ማለት ነው፡፡
ከአስኢት የቡኪ ድረስ በእግር አራት ቀን ይፈጃል፡፡ ወደ ውጭ ሃገር ለመሰደድ የሚጓዙ ወጣቶች ለሚረከቧቸው ደላሎች ሁሉ የያዙትን ገንዘብ በየደረጃው እየሰጡ ነው የሚጓዙት፡፡
ከመካከላቸው አንድ ስደተኛ ይማም ይባላል፡፡ ወደ አረብ ሃገር ከዚህ በፊትም ተሰዶ ሳይሳካለት ከየመን ተመልሷል፡፡ ለእሱ ስደት አዲሱ አይደለም፡፡ በስደት ላይ ምን አይነት ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡
"ገንዘባችሁን ሽፍቶች እንዳይዘርፏችሁ፡፡ ሲፈተሸ በማይገኝበት ቦታ መደበቅ አለባችሁ፡፡ አለ ይማም፡፡ አብረውት ለሚጎዙት ጓደኞቹ ፡፡ ወንዶቹ በልብሳቸው ጠርዝ እና የለበሱትን ሸበጥ በምላጭ በመሰንጠቅ አመሳስለው ሰፉት፡፡
ሴቶቹ ደግሞ እንደ ወንዶቹ የልብስ ጠርዛቸውንና ጫማዎቻቸውን ባይጠቀሙም የያዙትን ገንዘብ በስስ ፌስታል እየጠቀለሉ በብልታቸው ውስጥ ከተቱት፡፡
ከአስኢት እና የቡኪ መካከል ለስደተኛ መቅጫ የተፈጠረ ይመስላል፡፡ የአፋርና የጅቡቲን ሽፍቶች በውስጡ አቅፎ የሚኖር የገመሪ ተራራ፡፡ በጨለማ ለተመለከተው መሬት አልቃ የሰማይ ጥግ የደረሱ ይመስል ነበር፡፡ የገመሪን ተራራ ብቻ በእግር ለመውጣት ከሶስት ሰዓታት በላይ ይፈጃል፡፡ ሃያ የኢትዮጵያ ስደተኞች ተመስገንና እድላዊትን ጨምሮ የገመሪን ተራራ ለመውጣት ትንቅንቅ ገብተዋል፡፡
በውሃ ጥም እና በድካም የሞቱ የስደተኞች አስከሬን በተራራው ፣ በየእንጨቱ ላይ ተንጠልጥሎ ስጋቸው የአሞራ ምሳ ሆኗል ፡፡ ሲያዩት ተደናገጡ፡፡ ከነመፈጠራቸውም አምርረው ረገሙ፡፡ የገመሪን ተራራ በአራት እግራቸው እየዳሁ ስቃይና መከራቸውን አብዝቶታል፡፡
ተንቀሳቃሹ የቁም ስቃይና መከራ የሚያሳዩት የአፋርና የጅቡቲ ሽፍቶች ረሃብ እንደሰነበተበት የበርሃ ጅብ ከፊት ለፊታቸው ድቅን አሉባቸው፡፡
የመሳሪያ አፈሙዝ ደቀኑባቸው፡፡ በበረሃ ልምጭ ገንዘብ አምጡ እያሉ ገረፏቸው፡፡ እግዚአብሔር እባብን ፈጥሮ የአዳም ልጆች ራስ ራሱን እንዲቀጠቅጡት እንደተፈረደበት ተቀጠቀጡ፡፡
በኪሳቸው ያገኙትን ገንዘብ ሁሉ ቀሟቸው፡፡ ሽፍቶቹ በገንዘብ ብቻ አልተመለሱም፡፡ ሴቶችን እየገረፉ አሰቃዩዋቸው፡፡ ልብሳቸውን አስወለቋቸው፡፡
የደበቁትን ገንዘብ እንዳይወሰድባቸው ልብሳቸውን ሲያወልቁ ከፓንታቸው ጋር አመሳስለው በማውለቅ ቢያተርፉትም፡፡ መደፈሩ ግን አልቀረላቸውም፡፡
የጠይም መልከ መልካሟ እድላዊት ለሽፍቶች አለቃ በሞግዚቶቹ ተመርጣ ቀረበች፡፡ አይኖቿ በእንባ ተሞሉ፡፡ ተቁለጨለጨች፡፡ ጨካኙ የሽፍቶች አለቃ አላዘነላትም፡፡ እየረገጠና እያዳፋ ልብሷን አስወለቃት፡፡ እንደ እሳት በሚጋረፈው የገመሪ የፀሃይ ሃሩር እርቃነ ስጋዋን አስቀራት፡፡ አንዴ አፈንድጅ ፣ አንዴ ተገልበጭ እያለ አሰቃያት፡፡ ብልቱ የተለበለበ ማረሻ ይመስላል፡፡ ሊደፍራት ብልቱን አስጠጋ፡፡
እድላዊት ድንገት ከብልቷ የደም ፈሳሽ ፈሰሳት፡፡ እንዳፈነደደች በርግጫ ከመሬት ቀላቀላት፡፡ ወደ ሌሎች ስደተኞች ተመለሰ፡፡
ቅንጣት የሚያክል ርህርሄ የሌላቸው ወንበዴዎች እንደ አስፈለጋቸው የልባቸውን አድርሰው ለቀቋቸው፡፡
ከዘጠኙ ሴቶች አራቱ በደረሰባቸው አስገድዶ መድፈርና ድብደባ ህይወታቸው ወዲያውኑ አለፈ፡፡
የተቀሩት አምስት ሴቶች እድላዊትን ጨምሮ መትረፍ ሳይሆን ለመሰንበት ያክል ነብሳቸው ተረፈች፡፡
በውሃ ጥምና ረሃብ ተሰቃይተው የሽፍታ ዱላ እንደ እናታቸው ጠግበው መሄድ አቅቷቸው በጣረሞት ትንሽ እንደተጓዙ ሁለት ወጣት ወንዶች በመንገድ ላይ ህይወታቸው ተቀጠፈ፡፡ ቢደክማቸውም በእንጨት መሬት ቆፍረው ቀበሯቸው፡፡ ተለቃቅሰው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡
እድላዊት በደረሰባት አሰቃቂ ድብደባ ደከማት፡፡ መሄድ አቅቷታል፡፡ መንገድ ላይ ወደቀች፡፡ አብረዋቸው የነበሩ ጥለዋቸው ሄዱ፡፡ ተመስገን ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ የሚያቀምሳት በእጁ ላይ ምንም አልነበረም፡፡ ከቤት ሲወጡ ያዘጋጁትን ስንቅም ሳያስቀሩ የጅቡቲ ሽፍቶች ዘርፈዋቸዋል፡፡ ትንሽ አረፍ እንዳለች ትንፋሿ መለስ አለላት፡፡ እንሂድ ሌላ ሽፍታ ሳይመጣብን አለች፡፡ አብሯት ለቀረው ተመስገን፡፡
የሞት ሞቷን ተነሳች፡፡ ጥለዋቸው የሄዱትን ጓደኞቻቸውን የቡኪ ደረሱባቸው፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
የገመሪ ተራራ
የተደበቀው ሚስጥር እንዳይወጣበት ከዛሬ ነገ እያለ እንደሌባ በሩቁ ይሸሻል፡፡ የሱ ጉዳዩ ከተፈፀመለት በኋላ፤ ተመልሶ ወደ ያሬድ ቤት አልሄደም፡፡ ጓደኛው ወደ ውትድርና መግባቱን ሲሰማ ስጋትና
ጭንቀት አላስቀመጠውም፡፡ የአበበችን ዓይን ማየት አልቻለም፡፡
ያለውን ንብረት እንዳይነቃበት በከፊል ሸጠ፡፡ ከእድላዊት ጋር ሃገር ለቀው ለመሄድ ተስማሙ፡፡ ለመንገድ የሚሆን በሶና ቆሎ አዘጋጁ፡፡ ስደትን መርጠዋል፡፡ ልጃቸውንና እናት አባታቸውን ያለጧሪ ፣ ቀባሪ ትተው ለመሄድ ተነሱ፡፡ አንጀታቸው አዘነ፡፡ አይናቸው አነባ፡፡ ልባቸው ግን ጨክኗል፡፡ ቤተሰቦቻቸውን ፀበል ነው የምንሄደው ብለው ዋሽተዋቸዋል፡፡ ጨለማ በተቀላቀለበት ሌሊት በዕለተ ሰንበት ሰው ወደ ቤተክርስትያን ለመሳም በሚሄድበት ሰዓት እነሱ ወደ አረብ ሃገር ስደት ሆነ፡፡ ከሰም ጅረቱን አቋርጠው በደብረብርሃን አድርገው ወደ ወሎ ባቲ ተጓዙ፡፡
ከሶስት ቀን ጎዞ በኋላ ባቲ ከተማ እንደደረሱ በቀይ ሸራ ወደ ተሸፈነች የሻይ ድንኳን ጎራ አሉ፡፡
በጦስኝ ቅመም የተንቆጠቆጠ የባቲ ሻይ አዘዙ፡፡
አንድ መልከ መልካም ወጣት ወደ ሻይ ቤቷ ገባ፡፡
"ቶሎ በል አንድ ሻይ በዳቦ ስጠኝ ? ሰዎች እየጠበቁኝ ነው አለ ፤ ወጣቱ እየተጣደፈ፡፡
የሻይ አስተናጋጁ "እነማን ናቸው የሚጠብቁህ"? አለ፡፡
ወደ አረብ ሃገር የሚሄዱ ናቸው፡፡ ከመሃመድ ጋር አገናኝቻቸው ልመጣ ነው አለ፡፡ ያዘዘውን ሻይና ዳቦውን ሲበላ ለተመለከተው የቸኮለ ሰው ሳይሆን ከጎሬ የወጣ ጅብ ይመስል ነበር፡፡
ወደ አረብ ሃገር በየት እንደሚኬድ አያውቁም፡፡
"ይሄንን ልጅ እንጠይቀው" ? አለች እድላዊት፡፡ ወጣቱ ስለ አረብ ሃገር ሲያወራ ሰምታ፡፡
ተመስገን ለመጠየቅ ፈራ ተባ አለ፡፡ ኧረ! ለመሄድ ተቻኩሏል ሳይነሳ ጠይቀው አለች ? ደግማ፡፡
"ወንድም" ? አለ ፤ ተመስገን፡፡ ከሻይና ከዳቦ ጋር እየታገለ ያለውን ወጣት፡፡
"አቤት ጠራኸኝ" ? አለ ፤ ወጣቱ፡፡
"አዎ፤ አንድ ነገር ትተባበረኛለህ ?፡፡
አላመነታም፡፡ "ምን ልተባበራችሁ? ወደ አረብ ሃገር መሄድ ትፈልጋላችሁ? ፡፡
"አዎ፤ ለመሄድ ፈልገን ነበር ፡፡
"እኔ ደላላ ነኝ፡፡ ከሚልከው ሰው ጋር እንዳገናኛችሁ፡፡ ከፈለጋችሁ ሁለታችሁም አርባ አርባ ብር ክፈሉኝ ብሎ ለመሄድ ተነሳ፡፡
"እሽ እንከፍልሃለን፡፡ ታዲያ አሁን የት ልትሄድ ነው? አለው፡፡
"ሰው እየጠበቀኝ ነው፡፡ ቼኩያዓለሁ ፤ ከሄዳችሁ ብሩን አምጡና ተነሱ እንሂድ አላቸው፡፡
"እሽ" አሉ፡፡ የያዙትን ገንዘብ ከፍለው ደላላውን ተከተሉት፡፡
ወደ ውጭ ሃገር የሚልኳቸውን የሰዎች ማሰባሰቢያ ቤት ደረሱ፡፡ መሃመድ ለሚባል ደላላ አስረክቧቸው ተመለሰ፡፡
መሃመድ ተቀብሎ ወደ ውጭ ሃገር ሊወስዳቸው ካሰባሰባቸው ስምንት ሴትና አስር ወንዶች ጋር ቀላቅሎ በራሱ መኪና አሳፍሮ አስኢት ከተማ አደረሳቸው፡፡
እሱም ለአስኢት ደንበኛው ለከድር አስረክቧቸው ተመለሰ፡፡
የአስኢት ደላላው ከድር ከመሃመድ ዘጠኝ ሴቶችንና አስራ አንድ ወንዶችን በድምሩ ሃያ ሰዎችን ተቀብሎ ከአስኢት ከተማ ጉዞ በምሽት ጫካ ለጫካ በእግር ወደ የቡኪ ተጀመረ፡፡
የቡኪ የኢትዮጵያ አፋር መሬትን ጨርሶ የጅቡቲ መዳረሻ መሬት ማለት ነው፡፡
ከአስኢት የቡኪ ድረስ በእግር አራት ቀን ይፈጃል፡፡ ወደ ውጭ ሃገር ለመሰደድ የሚጓዙ ወጣቶች ለሚረከቧቸው ደላሎች ሁሉ የያዙትን ገንዘብ በየደረጃው እየሰጡ ነው የሚጓዙት፡፡
ከመካከላቸው አንድ ስደተኛ ይማም ይባላል፡፡ ወደ አረብ ሃገር ከዚህ በፊትም ተሰዶ ሳይሳካለት ከየመን ተመልሷል፡፡ ለእሱ ስደት አዲሱ አይደለም፡፡ በስደት ላይ ምን አይነት ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡
"ገንዘባችሁን ሽፍቶች እንዳይዘርፏችሁ፡፡ ሲፈተሸ በማይገኝበት ቦታ መደበቅ አለባችሁ፡፡ አለ ይማም፡፡ አብረውት ለሚጎዙት ጓደኞቹ ፡፡ ወንዶቹ በልብሳቸው ጠርዝ እና የለበሱትን ሸበጥ በምላጭ በመሰንጠቅ አመሳስለው ሰፉት፡፡
ሴቶቹ ደግሞ እንደ ወንዶቹ የልብስ ጠርዛቸውንና ጫማዎቻቸውን ባይጠቀሙም የያዙትን ገንዘብ በስስ ፌስታል እየጠቀለሉ በብልታቸው ውስጥ ከተቱት፡፡
ከአስኢት እና የቡኪ መካከል ለስደተኛ መቅጫ የተፈጠረ ይመስላል፡፡ የአፋርና የጅቡቲን ሽፍቶች በውስጡ አቅፎ የሚኖር የገመሪ ተራራ፡፡ በጨለማ ለተመለከተው መሬት አልቃ የሰማይ ጥግ የደረሱ ይመስል ነበር፡፡ የገመሪን ተራራ ብቻ በእግር ለመውጣት ከሶስት ሰዓታት በላይ ይፈጃል፡፡ ሃያ የኢትዮጵያ ስደተኞች ተመስገንና እድላዊትን ጨምሮ የገመሪን ተራራ ለመውጣት ትንቅንቅ ገብተዋል፡፡
በውሃ ጥም እና በድካም የሞቱ የስደተኞች አስከሬን በተራራው ፣ በየእንጨቱ ላይ ተንጠልጥሎ ስጋቸው የአሞራ ምሳ ሆኗል ፡፡ ሲያዩት ተደናገጡ፡፡ ከነመፈጠራቸውም አምርረው ረገሙ፡፡ የገመሪን ተራራ በአራት እግራቸው እየዳሁ ስቃይና መከራቸውን አብዝቶታል፡፡
ተንቀሳቃሹ የቁም ስቃይና መከራ የሚያሳዩት የአፋርና የጅቡቲ ሽፍቶች ረሃብ እንደሰነበተበት የበርሃ ጅብ ከፊት ለፊታቸው ድቅን አሉባቸው፡፡
የመሳሪያ አፈሙዝ ደቀኑባቸው፡፡ በበረሃ ልምጭ ገንዘብ አምጡ እያሉ ገረፏቸው፡፡ እግዚአብሔር እባብን ፈጥሮ የአዳም ልጆች ራስ ራሱን እንዲቀጠቅጡት እንደተፈረደበት ተቀጠቀጡ፡፡
በኪሳቸው ያገኙትን ገንዘብ ሁሉ ቀሟቸው፡፡ ሽፍቶቹ በገንዘብ ብቻ አልተመለሱም፡፡ ሴቶችን እየገረፉ አሰቃዩዋቸው፡፡ ልብሳቸውን አስወለቋቸው፡፡
የደበቁትን ገንዘብ እንዳይወሰድባቸው ልብሳቸውን ሲያወልቁ ከፓንታቸው ጋር አመሳስለው በማውለቅ ቢያተርፉትም፡፡ መደፈሩ ግን አልቀረላቸውም፡፡
የጠይም መልከ መልካሟ እድላዊት ለሽፍቶች አለቃ በሞግዚቶቹ ተመርጣ ቀረበች፡፡ አይኖቿ በእንባ ተሞሉ፡፡ ተቁለጨለጨች፡፡ ጨካኙ የሽፍቶች አለቃ አላዘነላትም፡፡ እየረገጠና እያዳፋ ልብሷን አስወለቃት፡፡ እንደ እሳት በሚጋረፈው የገመሪ የፀሃይ ሃሩር እርቃነ ስጋዋን አስቀራት፡፡ አንዴ አፈንድጅ ፣ አንዴ ተገልበጭ እያለ አሰቃያት፡፡ ብልቱ የተለበለበ ማረሻ ይመስላል፡፡ ሊደፍራት ብልቱን አስጠጋ፡፡
እድላዊት ድንገት ከብልቷ የደም ፈሳሽ ፈሰሳት፡፡ እንዳፈነደደች በርግጫ ከመሬት ቀላቀላት፡፡ ወደ ሌሎች ስደተኞች ተመለሰ፡፡
ቅንጣት የሚያክል ርህርሄ የሌላቸው ወንበዴዎች እንደ አስፈለጋቸው የልባቸውን አድርሰው ለቀቋቸው፡፡
ከዘጠኙ ሴቶች አራቱ በደረሰባቸው አስገድዶ መድፈርና ድብደባ ህይወታቸው ወዲያውኑ አለፈ፡፡
የተቀሩት አምስት ሴቶች እድላዊትን ጨምሮ መትረፍ ሳይሆን ለመሰንበት ያክል ነብሳቸው ተረፈች፡፡
በውሃ ጥምና ረሃብ ተሰቃይተው የሽፍታ ዱላ እንደ እናታቸው ጠግበው መሄድ አቅቷቸው በጣረሞት ትንሽ እንደተጓዙ ሁለት ወጣት ወንዶች በመንገድ ላይ ህይወታቸው ተቀጠፈ፡፡ ቢደክማቸውም በእንጨት መሬት ቆፍረው ቀበሯቸው፡፡ ተለቃቅሰው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡
እድላዊት በደረሰባት አሰቃቂ ድብደባ ደከማት፡፡ መሄድ አቅቷታል፡፡ መንገድ ላይ ወደቀች፡፡ አብረዋቸው የነበሩ ጥለዋቸው ሄዱ፡፡ ተመስገን ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ የሚያቀምሳት በእጁ ላይ ምንም አልነበረም፡፡ ከቤት ሲወጡ ያዘጋጁትን ስንቅም ሳያስቀሩ የጅቡቲ ሽፍቶች ዘርፈዋቸዋል፡፡ ትንሽ አረፍ እንዳለች ትንፋሿ መለስ አለላት፡፡ እንሂድ ሌላ ሽፍታ ሳይመጣብን አለች፡፡ አብሯት ለቀረው ተመስገን፡፡
የሞት ሞቷን ተነሳች፡፡ ጥለዋቸው የሄዱትን ጓደኞቻቸውን የቡኪ ደረሱባቸው፡፡
👍54❤10😱2
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
የተዳፈነ እሳት
ከሁለት አጉል ሆነች፡፡ እንደ ባህር ላይ ኩበት ተንሳፈፈች፡፡ ከባለቤቷ ወይም ከቤተሰቦቿ ሳትሆን ቀረች፡፡ ባለቤቷ ለገበያ እንደሄደ ወደ ውትድርና መግባቱን ሰማች፡፡ የመኖር ተስፋዋ እንደ ተዳፈነ እሳት ውስጧ ተንቦገቦገ፡፡ የጨለማ ተከናነበ፡፡ ከባለቤቷ ጋር ሰርታ የመለወጥ ተሰፋዋ ከማህል ተቀጨ፡፡ የኑሮዋ መሻሻል ከጨለማ የመውጫ መንገድ ሳይሆን የጨለማ መግቢያ ሆናት፡፡ ቤተሰቦቿ ባላወቁት ጉዳይ አይንሽን ላፈር አሏት፡፡
ታዲያ አበበች አስቀድማም እንደሚገጥማት ብገምትም ለሰው መልካም ነገር ማድረግ ግን እንደዚህ የእሳት እረመጥ ይሆንብኛል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የመከራ ፅዋ ተጎንጭታ፡፡ ገና እናትና አባቱን እንኳን በደንብ ካለየ ህፃን ልጇ ጋር ያለ ዘመድና ያለ አይዞሽ ባይ ባዶ ቤት ለመኖር ተገደደች፡፡ ስታለቅስ ውላ ስታለቅስ ብታድርም ከልጅዋ በስተቀር አብሯት የሚያለቅስ ሰው አይደለም ወደ ቤቷ ዝር ብሎ አይዞሽ የሚላት እንኳን አልነበረም፡፡
ከእለታት አንድ ቀን የያሬድ አጎት አቶ አስፋው ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የኔነሽ ጋር ቡና አፍልተው እየጠጡ ነው፡፡
"እንዴው ያችን የያሬድ ባለቤት ሳንጠይቃት ምን ትለን ይሆን ? ቤተሰቦቿም እደጃችንም እንዳትደርሽ ብለዋታል አሉ፡፡ ያሬድም ብቻዋን ባዶ ቤት አዳፍኖባት ወዶ ዘማች መሄዱ የሚገርም ነው" አሉ፡፡ አቶ አስፋው ፤ በጉንጫቸው ላይ የወረደውን ረጃጅም ፂማቸውን በእጃቸው እየደባበሱ፡፡
"ምን ተጠየቀች አልተጠየቀች ምን ጎሎባታል፡፡ ያለውን ንብረት ጥሎላት ነው የሄደው፡፡ እሷን ደግሞ ማን ይጠይቃታል፡፡ እቤት ተቀምጣ ባሏን ሳይሞት በቁሙ የገፋች ገፊ" አሉ፡፡ ምንም አዘኔታ እንኳን ሳይታይባቸው፡፡ ግን የአበበችን በደልና ስቃይ ቢያውቁ ኖሮ እንደዚህ ባልተናገሩ ነበር፡፡
አቶ አስፋው በሰል ያሉና ብዙ ውጣ ውረዶችን በትንሹም ቢሆን መከራና ስቃይን ያሳለፉ በመሆናቸው ለተጎዳ ሰው የሚያስቡና ትህትና ያላቸው ማለፊያ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ የባለቤታቸው ንግግር አልተዋጠላቸውም፡፡
አይ! አንች ከንቱ መሆንሽ ያሳዝናል፡፡ ለነገሩ የችግርን ነገር ስለማታውቂው አይፈረድብሽም፡፡
የአንች ነገር በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት እንደ ሚባለው ነው፡፡ በአንች ላይ ቢደርስብሽ ያኔ በደንብ ታውቂው ነበር አሉ፡፡
ምን የተባለውንና የተወራውን ነው፡፡ የተናገርኩት በእሷም የተነሳ አይደለም እንዴ፡፡ ወንድሟ ያሬድን ለመግደል እያደፈጠ ሲስተው የነበረው፡፡ ታዲያ ይህ አገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው አይደለም አሉ፡፡ ስኒ አጣጥበው እረከቦት ላይ እያደረጉ፡፡
"ዝም ብለሽ በማታውቂው ነገር ትዘላብጃለሽ፡፡ ያሬድ የተሳሳተው በራሱ ልክስክስነት እንጂ በአበበች ጥፋት አይደለም፡፡ እሷ ምን አጠፋች ባሌ ዲቃላ ቢወልድም እሱ ይሻለኛል፡፡ ስላለች አይደለም አባቷ አይንሽን ላፈር ያሏት፡፡ ለማንኛውም ምንም ቢሆንዐተዋልደናልና የእሷ ቤተሰቦች እንኳን ቢጠሏት ደግሞ በራሳችን ጥፋት ልንሸሻት አይገባም፡፡
ደግመውም ሌላ ንግግር ሳይነጋገሩ በይ እስቲ አሁን በቁሜ ቢሆን ደረስ ብዬ ልምጣ ብለው ዘንጋቸውን ይዘው ተነስተው ወደ አበበች ቤት ሔዱ፡፡
ቤቱ ተዘግቶ በግቢው ውስጥ ሰው አይደለም ከብትም አላገኙም፡፡ አቶ አስፋው፡፡ ወዴት ሔዳ ይሆን ? ቆይታ ይሆን ከሄደች ? እያሉ ግራ በመጋባት ከራሳቸው ሐሳብ ጋር እየተሟገቱ ወደ መጡበት ተመለሱ፡፡
አበበች ልጇን አዝላ ውሃ ቀድታና ከብቶቿን አጠጥታ ከወንዝ ስትመጣ ከአቶ አስፋው ጋር እመንገድ ላይ ተገናኙ፡፡
"ደህና ዋልሽ አበበች" ? አሏት አቶ አስፋው፡፡
እግዚአብሔር ሰላም ዋሉ ? አለች፡፡ አይኗን ወደ አቶ አስፋው አትኩራ እየተመለከተች፡፡
"እኔ እኮ እቤት ሄጄ ቤቱ ተዘግቶ ሳይ የት ሄደች ብየ ስመለስ ነው ያገኘሁሽ" አሉ፡፡
"ምን ላድርገው አንዴ ያደለኝን ከብት እንኳን የሚያጠጣልኝ ሰው አጣሁ፡፡ ችግር ሲደርስብኝ እንኳን ዞር ብሎ የሚያዬኝ ጠፋ፡፡ እግዚአብሔርም ጨከነብኝ አለች፡፡
"እኔም ዛሬ ነገ እያልኩ ሳልመጣና ሳልጠይቅሽ ቀረሁ፡፡ ብትቀየምም ዛሬ አይቻት ልምጣ ብዬ ነው የመጣሁት፡፡ ሰው በቁሙ ካልተረዳዳ ከሞተ በኋላ ዋይ ዋይ ቢሉት ተመልሶ አይመጣም፡፡ እንዴው ሰራተኛ አላገኝሽም ኖሯል? አሉ፡፡
አይ! ጋሸ አስፋው የት አገኛለሁ ሰራተኛ የሚገኘው ከሰው ሲገናኙ ነው፡፡ እኔ ከሰው አልገናኝ፡፡ ዘመዶቸም ጠልተውኛል፡፡ አሁን ደግሞ አዝመራ እየደረሰ ነው፡፡ ማሳውን ማን እንደሚያርስልኝ ጨንቆኛል፡፡ ብን ብየ እንዳልጠፋ ይሄን ጨቅላ ልጅ አቅፌ መሄዱ ከበደኝ፡፡… ልማደኛው እንባዋ ተናንቋት አለቀሰች፡፡
በቃሽ አታልቅሽ ተይ፡፡ አንች እያለቀስሽ ምንም የማያቀውን ህፃን አታስለቅሽ፡፡ ያሬድም እንደሆነ ይመጣል፡፡ ወዶ ዘማች የሄደ ሁሉ አይሞትም፡፡ ለሁሉም እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ ዛሬ ቢጨልምም ነገ መንጋቱ አይቀርም፡፡ አይዞሽ፡፡ አዝመራውም ይዘመራል፡፡ ነገ ወደ ሸንኮራ ዮሃንስ መሄዴ ስለማይቀር ሰራተኛ እዠልሽ እመጣለሁ፡፡
ደግሞም የሚቸግርሽ ነገር ካለ እኔም ቢሆን እየመጣሁ አግዝሻለሁ፡፡ በነጋ በጠባ ቁጥር ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ እግዚአብሔርም አይወድም፡፡ እባክሽን ለልጅሽ ስትይ አታልቅሽ፡፡ አንችም ያለ እድሜሽ በሽታ ላይ ትወድቂያለሽ፡፡ ብለው አፅናንተዋት ተነስተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ትንሽ የነበረባት የጭንቀት ጨለማ ፈገግ ያለ መሰላት፡፡ አቶ አስፋው አይዞሽ ብለዋት ሲሄዱ፡፡ ባለቤቷ ወዶ ዘማች በመግባቱ መልሳ በህይወት የምታገኘው ግን አልመስል አላት፡፡ ፈገግ ብሎ የነበረው የጨለማ ብርሃን መልሶ ይጨልምባታል፡፡
አበበች ሁለተኛ ልጇን መፀነሷን የታወቃት ያሬድ በሄደ በሁለተኛው ሳምንት የወር አበባዋ ሲቋረጥ ነበር፡፡
አቶ አስፋው ለአበበች በገቡላት ቃል መሰረት ሰራተኛ አግኝተው ቀጠሩላት፡፡ ባለቤቷ ያሬድ እንደነበረው ጊዜ የተደላደለ ህይወትን ባትኖርም በባዶ ቤት ሆና ከምታለቅሰው የተሻለ ህይወት መኖር ጀመረች፡፡
የቤተሰቦቿ መጥላት ሳያንሳት የተመስገን እናት ወ/ሮ አሰገደች ሲወጡና ሲገቡ የባልሽን ዲቃላ አሳዳጊ አደረግሽኝ ፡፡ ባልሽም ዲቃላውን እንዳይወስድ የሰራው ስራ አሳፍሮት አገር ለቆ ጠፋ፡፡ እያሉ አላስገባ አላስወጣ አሏት፡፡ አበበች ግን አልቅሳ ዝም ከማለት ውጭ ምንም ምላሽ አልነበራትም፡፡
ጉልላት የተባለው የአበበች ሰራተኛ ትንሽ ጠና ያለና ነብስ አወቅ ያደረገ ነው፡፡ አበበች ስታለቅስና ስትበሳጭ አይዞሽ እያለ እያፅናና ያበረታታል፡፡
ጉልላት ለሁሉ ታዛዥ ቅን ሰው ለመሆኑ ደከመኝ ሰለቼኝ ሳይል ሲያገለግላት ላየውና ለተመለከተው የእናት ልጅ እንኳን እንደሱ አድርጎ የሚሰራ አይመስልም ነበር፡፡
አበበች ባለቤቷ ያሬድ ከሄደ ከዘጠኝ ወር በኋላ አንድ ቀን በእለተ ሐሙስ በጥዋት ተነሳች፡፡ የሚሸጥ ስንዴ ቋጠረች፡፡ ለጉልላት ገበያ ልልከው አስባለች፡፡ ይሔን ስንዴ ሽጥና አንዳንድ ነገሮችን ግዛልኝና ና፡፡ እኔም ቀኔ ደርሷል ብላ የሚገዙትን የእቃ ዓይነቶች ነግራ ቁርሱን አብልታ ወደ ገበያ ላከችው፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
የተዳፈነ እሳት
ከሁለት አጉል ሆነች፡፡ እንደ ባህር ላይ ኩበት ተንሳፈፈች፡፡ ከባለቤቷ ወይም ከቤተሰቦቿ ሳትሆን ቀረች፡፡ ባለቤቷ ለገበያ እንደሄደ ወደ ውትድርና መግባቱን ሰማች፡፡ የመኖር ተስፋዋ እንደ ተዳፈነ እሳት ውስጧ ተንቦገቦገ፡፡ የጨለማ ተከናነበ፡፡ ከባለቤቷ ጋር ሰርታ የመለወጥ ተሰፋዋ ከማህል ተቀጨ፡፡ የኑሮዋ መሻሻል ከጨለማ የመውጫ መንገድ ሳይሆን የጨለማ መግቢያ ሆናት፡፡ ቤተሰቦቿ ባላወቁት ጉዳይ አይንሽን ላፈር አሏት፡፡
ታዲያ አበበች አስቀድማም እንደሚገጥማት ብገምትም ለሰው መልካም ነገር ማድረግ ግን እንደዚህ የእሳት እረመጥ ይሆንብኛል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡ አንዴ ያደላትን የመከራ ፅዋ ተጎንጭታ፡፡ ገና እናትና አባቱን እንኳን በደንብ ካለየ ህፃን ልጇ ጋር ያለ ዘመድና ያለ አይዞሽ ባይ ባዶ ቤት ለመኖር ተገደደች፡፡ ስታለቅስ ውላ ስታለቅስ ብታድርም ከልጅዋ በስተቀር አብሯት የሚያለቅስ ሰው አይደለም ወደ ቤቷ ዝር ብሎ አይዞሽ የሚላት እንኳን አልነበረም፡፡
ከእለታት አንድ ቀን የያሬድ አጎት አቶ አስፋው ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የኔነሽ ጋር ቡና አፍልተው እየጠጡ ነው፡፡
"እንዴው ያችን የያሬድ ባለቤት ሳንጠይቃት ምን ትለን ይሆን ? ቤተሰቦቿም እደጃችንም እንዳትደርሽ ብለዋታል አሉ፡፡ ያሬድም ብቻዋን ባዶ ቤት አዳፍኖባት ወዶ ዘማች መሄዱ የሚገርም ነው" አሉ፡፡ አቶ አስፋው ፤ በጉንጫቸው ላይ የወረደውን ረጃጅም ፂማቸውን በእጃቸው እየደባበሱ፡፡
"ምን ተጠየቀች አልተጠየቀች ምን ጎሎባታል፡፡ ያለውን ንብረት ጥሎላት ነው የሄደው፡፡ እሷን ደግሞ ማን ይጠይቃታል፡፡ እቤት ተቀምጣ ባሏን ሳይሞት በቁሙ የገፋች ገፊ" አሉ፡፡ ምንም አዘኔታ እንኳን ሳይታይባቸው፡፡ ግን የአበበችን በደልና ስቃይ ቢያውቁ ኖሮ እንደዚህ ባልተናገሩ ነበር፡፡
አቶ አስፋው በሰል ያሉና ብዙ ውጣ ውረዶችን በትንሹም ቢሆን መከራና ስቃይን ያሳለፉ በመሆናቸው ለተጎዳ ሰው የሚያስቡና ትህትና ያላቸው ማለፊያ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው፡፡ የባለቤታቸው ንግግር አልተዋጠላቸውም፡፡
አይ! አንች ከንቱ መሆንሽ ያሳዝናል፡፡ ለነገሩ የችግርን ነገር ስለማታውቂው አይፈረድብሽም፡፡
የአንች ነገር በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት እንደ ሚባለው ነው፡፡ በአንች ላይ ቢደርስብሽ ያኔ በደንብ ታውቂው ነበር አሉ፡፡
ምን የተባለውንና የተወራውን ነው፡፡ የተናገርኩት በእሷም የተነሳ አይደለም እንዴ፡፡ ወንድሟ ያሬድን ለመግደል እያደፈጠ ሲስተው የነበረው፡፡ ታዲያ ይህ አገር ያወቀው ፀሐይ የሞቀው አይደለም አሉ፡፡ ስኒ አጣጥበው እረከቦት ላይ እያደረጉ፡፡
"ዝም ብለሽ በማታውቂው ነገር ትዘላብጃለሽ፡፡ ያሬድ የተሳሳተው በራሱ ልክስክስነት እንጂ በአበበች ጥፋት አይደለም፡፡ እሷ ምን አጠፋች ባሌ ዲቃላ ቢወልድም እሱ ይሻለኛል፡፡ ስላለች አይደለም አባቷ አይንሽን ላፈር ያሏት፡፡ ለማንኛውም ምንም ቢሆንዐተዋልደናልና የእሷ ቤተሰቦች እንኳን ቢጠሏት ደግሞ በራሳችን ጥፋት ልንሸሻት አይገባም፡፡
ደግመውም ሌላ ንግግር ሳይነጋገሩ በይ እስቲ አሁን በቁሜ ቢሆን ደረስ ብዬ ልምጣ ብለው ዘንጋቸውን ይዘው ተነስተው ወደ አበበች ቤት ሔዱ፡፡
ቤቱ ተዘግቶ በግቢው ውስጥ ሰው አይደለም ከብትም አላገኙም፡፡ አቶ አስፋው፡፡ ወዴት ሔዳ ይሆን ? ቆይታ ይሆን ከሄደች ? እያሉ ግራ በመጋባት ከራሳቸው ሐሳብ ጋር እየተሟገቱ ወደ መጡበት ተመለሱ፡፡
አበበች ልጇን አዝላ ውሃ ቀድታና ከብቶቿን አጠጥታ ከወንዝ ስትመጣ ከአቶ አስፋው ጋር እመንገድ ላይ ተገናኙ፡፡
"ደህና ዋልሽ አበበች" ? አሏት አቶ አስፋው፡፡
እግዚአብሔር ሰላም ዋሉ ? አለች፡፡ አይኗን ወደ አቶ አስፋው አትኩራ እየተመለከተች፡፡
"እኔ እኮ እቤት ሄጄ ቤቱ ተዘግቶ ሳይ የት ሄደች ብየ ስመለስ ነው ያገኘሁሽ" አሉ፡፡
"ምን ላድርገው አንዴ ያደለኝን ከብት እንኳን የሚያጠጣልኝ ሰው አጣሁ፡፡ ችግር ሲደርስብኝ እንኳን ዞር ብሎ የሚያዬኝ ጠፋ፡፡ እግዚአብሔርም ጨከነብኝ አለች፡፡
"እኔም ዛሬ ነገ እያልኩ ሳልመጣና ሳልጠይቅሽ ቀረሁ፡፡ ብትቀየምም ዛሬ አይቻት ልምጣ ብዬ ነው የመጣሁት፡፡ ሰው በቁሙ ካልተረዳዳ ከሞተ በኋላ ዋይ ዋይ ቢሉት ተመልሶ አይመጣም፡፡ እንዴው ሰራተኛ አላገኝሽም ኖሯል? አሉ፡፡
አይ! ጋሸ አስፋው የት አገኛለሁ ሰራተኛ የሚገኘው ከሰው ሲገናኙ ነው፡፡ እኔ ከሰው አልገናኝ፡፡ ዘመዶቸም ጠልተውኛል፡፡ አሁን ደግሞ አዝመራ እየደረሰ ነው፡፡ ማሳውን ማን እንደሚያርስልኝ ጨንቆኛል፡፡ ብን ብየ እንዳልጠፋ ይሄን ጨቅላ ልጅ አቅፌ መሄዱ ከበደኝ፡፡… ልማደኛው እንባዋ ተናንቋት አለቀሰች፡፡
በቃሽ አታልቅሽ ተይ፡፡ አንች እያለቀስሽ ምንም የማያቀውን ህፃን አታስለቅሽ፡፡ ያሬድም እንደሆነ ይመጣል፡፡ ወዶ ዘማች የሄደ ሁሉ አይሞትም፡፡ ለሁሉም እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ ዛሬ ቢጨልምም ነገ መንጋቱ አይቀርም፡፡ አይዞሽ፡፡ አዝመራውም ይዘመራል፡፡ ነገ ወደ ሸንኮራ ዮሃንስ መሄዴ ስለማይቀር ሰራተኛ እዠልሽ እመጣለሁ፡፡
ደግሞም የሚቸግርሽ ነገር ካለ እኔም ቢሆን እየመጣሁ አግዝሻለሁ፡፡ በነጋ በጠባ ቁጥር ማልቀስ ጥሩ አይደለም፡፡ እግዚአብሔርም አይወድም፡፡ እባክሽን ለልጅሽ ስትይ አታልቅሽ፡፡ አንችም ያለ እድሜሽ በሽታ ላይ ትወድቂያለሽ፡፡ ብለው አፅናንተዋት ተነስተው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡
ትንሽ የነበረባት የጭንቀት ጨለማ ፈገግ ያለ መሰላት፡፡ አቶ አስፋው አይዞሽ ብለዋት ሲሄዱ፡፡ ባለቤቷ ወዶ ዘማች በመግባቱ መልሳ በህይወት የምታገኘው ግን አልመስል አላት፡፡ ፈገግ ብሎ የነበረው የጨለማ ብርሃን መልሶ ይጨልምባታል፡፡
አበበች ሁለተኛ ልጇን መፀነሷን የታወቃት ያሬድ በሄደ በሁለተኛው ሳምንት የወር አበባዋ ሲቋረጥ ነበር፡፡
አቶ አስፋው ለአበበች በገቡላት ቃል መሰረት ሰራተኛ አግኝተው ቀጠሩላት፡፡ ባለቤቷ ያሬድ እንደነበረው ጊዜ የተደላደለ ህይወትን ባትኖርም በባዶ ቤት ሆና ከምታለቅሰው የተሻለ ህይወት መኖር ጀመረች፡፡
የቤተሰቦቿ መጥላት ሳያንሳት የተመስገን እናት ወ/ሮ አሰገደች ሲወጡና ሲገቡ የባልሽን ዲቃላ አሳዳጊ አደረግሽኝ ፡፡ ባልሽም ዲቃላውን እንዳይወስድ የሰራው ስራ አሳፍሮት አገር ለቆ ጠፋ፡፡ እያሉ አላስገባ አላስወጣ አሏት፡፡ አበበች ግን አልቅሳ ዝም ከማለት ውጭ ምንም ምላሽ አልነበራትም፡፡
ጉልላት የተባለው የአበበች ሰራተኛ ትንሽ ጠና ያለና ነብስ አወቅ ያደረገ ነው፡፡ አበበች ስታለቅስና ስትበሳጭ አይዞሽ እያለ እያፅናና ያበረታታል፡፡
ጉልላት ለሁሉ ታዛዥ ቅን ሰው ለመሆኑ ደከመኝ ሰለቼኝ ሳይል ሲያገለግላት ላየውና ለተመለከተው የእናት ልጅ እንኳን እንደሱ አድርጎ የሚሰራ አይመስልም ነበር፡፡
አበበች ባለቤቷ ያሬድ ከሄደ ከዘጠኝ ወር በኋላ አንድ ቀን በእለተ ሐሙስ በጥዋት ተነሳች፡፡ የሚሸጥ ስንዴ ቋጠረች፡፡ ለጉልላት ገበያ ልልከው አስባለች፡፡ ይሔን ስንዴ ሽጥና አንዳንድ ነገሮችን ግዛልኝና ና፡፡ እኔም ቀኔ ደርሷል ብላ የሚገዙትን የእቃ ዓይነቶች ነግራ ቁርሱን አብልታ ወደ ገበያ ላከችው፡፡
👍53❤2
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ሚስጥሩ
ከአራት ዓመት ከውጊያ በኋላ፡፡ እንደ ማንኛውም የሰራዊት አባላት ዓመታዊ የወር ፍቃድ ደረሰው፡፡ የታጠቀውን የመንግስት መሳሪያ ለቅርብ አመራሩ አስረከበ፡፡ የፍቃድ ወረቀት ተቀበለ፡፡ የትግል አጋሮቹ ወደ ቤተሰቦቹ ሸኙት፡፡
የወርሃዊ ፍቃድ የተሰጠው እለት አራት አመታትን እንዳልቆየ ባለቤቱንና ልጁን ቶሎ ደርሶ ለማየት አንድ ቀን ሌሊት አልነጋ አለው፡፡ ካሳለፈው አራት ዓመታት በላይ በአይኑ ላይ እንቅልፍ የሚባል እንኳን ሳያልፍ ፍጥጥ ብሎ አነጋ፡፡ የሌሊቱ እንቅልፍ ወደ ቀን ተቀይሮበታል፡፡ ከመኪና ወንበር እያወዛወዘ ያላትመዋል፡፡
ያሬድ ከሁለት ቀን የመኪና ጉዞ በኋላ፤ አመሻሽ ላይ የትውልድ ቀየው ደረሰ፡፡ ሰፈሩ ሁሉ ዓዲስ ሆነበት፡፡ አካባቢው ተቀያይሯል፡፡ ተገረመ ፤ ከቤቱ አካባቢ
ዳገቱ ላይ ሻንጣውን አውርዶ አረፍ አለ፡፡ አይኖቹን በእሱ ቤት ላይ ተከላቸው፡፡ የእሱ ቤት ሰርቶት እንደሄደ አላገኘውም፡፡ የጣራው ሳር እረግፏል፡፡
የግቢውም አጥር ወላልቋል፡፡ በውስጡ ሰው ያለበት አይመስልም፡፡ ቤተሰቦቹን የሚያገኝ አልመስል አለው፡፡ ሆዱ በፍራት ተዋጠ፡፡ አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ ወደ ወላለቀውና ፈራረሰው ቤቱ ተጠጋ፡፡
ከቤቱ ደጅ ላይ ሁለት ወንድ ህፃናት ልጆች እየቦረቁ ይጫወታሉ፡፡ አትኩሮ ተመለከታቸው፡፡ አንደኛው ህፃን ትልቅ እና ሰውነቱ ለወጥወጥ ቢልበትም የራሱ ልጅ ምትኩ እንደሆነ አልተጠራጠረም ነበር፡፡
ሁለተኛው ህፃን ግን የማን እንደሆነ ሊያውቀው አልቻለም፡፡ ወደ ሚጫወቱት ህፃናት ተጠግቶ ልጁን ምትክ ምትኩ? ብሎ ተጣራ፡፡ ህፃኖቹ የራስ የራሳቸውን እየተጨዋወቱ ከስራቸው ተጠግቶ የቆመውን ያሬድን አላዩትም ነበር፡፡ ህፃን ምትኩ መጫወቱን ትቶ ቀና አለ፡፡ በሰውነቱ ግዙፍ የሆነ ሰው አዬ፡፡ አባቱ እንደሆነ አያውቅም፡፡ ፈርቶ የወንድሙን የሁሉባንተን እጅ እየጎተተ ሸሽተው ወደ ቤት ገቡ፡፡
ምን ሁናችሁ ነው የምትሮጡት? ውሻ አባረራችሁ እንዴ ? አለች አበበች፡፡ ልጆቿ እየሮጡ ሲገቡ ደንግጣ፡፡
"ህፃን ምትኩ በተቆራረጠ ትንፋሽ ውሻ አይደለም ፤ መጥቷል" አላት፡፡
"የማን ሰው ነው የመጣው" ?፡፡
"አላውቀውም ሲያዩት ያስፈራል፡፡ ውጭና እይው እውጭ ቁሟል አላት፡፡ ውጭ ውጭውን እየተመለከተ፡፡
አበበች ውጭ እና እይው ሲላት የባሰ ድንጋጤ ጨመረባት፡፡ የሚያስፈራ ሰው ደግሞ ከየት መጣብኝ፡፡ እንዲያው አምላኬ ምን ልታሰማኝ ይሆን? ቤቴን ሰው አያውቀው፡፡ እንዲያው ሰርታ በላች ብለው ሊጨርሱኝ ይሆን? ከሰው ጋርም ባይሆን ከራሷ ጋር ያወራችው ነበር፡፡
ወደ ውጭ ብቅ አለች፡፡ እውነትም የሚያስፈራ ሰው ነው፡፡ የውጩን በር ከፍቶ ገባ፡፡ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ የሚያስፈራው ሰውየ እየቀረባት መጣ፡፡
ለአራት አመታት የተለያት ባለቤቷ ያሬድ ነው፡፡ ማመን አቃታት፡፡ለመራመድ እግሮቿ ተሳሰሩ፡፡ አይኖቿ ያሬድ ላይ እንደተተከሉ በናፍቆት እንባ ተሞሉ፡፡
አበበች በደረሰባት ስቃይና መከራ ተጎሰቋቁላለች፡፡ የሃያ አምስት አመት ወጣት መምሰሏ ቀርቶ የአምሳ አመት አሮጊት ሆናለች፡፡ ያሬድ አዘነ፡፡ እያለቀሰ ተጠመጠመባት፡፡ ቤቱ ከሃዘን እንባ ወደ ደስታ እንባ ተቀየረ፡፡ አበበች የደረሰባትን ስቃይና መከራ እንዲሁም ባለቤቷ ያሬድ ከሄደ ስለወለደችው ልጅ ሁሉባንተ አጫውታው ልጁም የራሱ እንደሆነ ነግራው አምኖ ተቀብሏት ፡፡ ያሳለፉትን ናፍቆትና ትዝታ እያስታወሱ ሲለቃቀሱና ሲያወሩ ቢቆዩም ስለተደበቀው ሚስጢር ምንም ነገር ሳያወሩ አድረው በማግስቱ ጥዋት ነበር፡፡
ቡና ተፈልቶ "እንዴት አደረግሽው ያንን ነገር ያላት ?
"የቱን ነገር ? አለች ጥያቄው ግራ አጋብቷት፡፡
"ሚስጢሩን ነዋ አላት"፡፡
"አይ! ምነው ሁሉንም ነገር ለማንም እንዳትነግሪ ብለኸኝ በባዶ ቤት ያለቤተሰብና ያለ ዘመድ አዳፍነህብኝ ሄደህ ፤ እንዴት ነው ሚስጢሩ የሚወጣው?፡፡ ይኸው ከዛን እለት ጀምሮ ተመስገን እኔ ደጀም አልደረሰም፡፡ እስካሁንም አላየሁት፡፡ ብላ የነበረውን ሁኔታ ስታነሳሳ ውስጧ ተረበሸ፡፡ የብሶት እንባ አለቀሰች፡፡
ያሬድ የሚለው የሚናገረውን ቢያጣ ግራ ቢገባውም፡፡ ከተመስገን ያልተገናኛችሁት እዚሁ እያለ ነው ወይስ ከሃገር ለቆ ነው? አለ፡፡
በፊቷ ላይ የሚወርደውን እንባ በፎጣዋ ጠረግ ጠረግ እያደረገች "እዚሁ እያለ ሲሸሸኝ ፣ ሲሸሸኝ ቆይቶ እህቱን እድላዊትን ወደ ፀበል ልወስዳት ነው፡፡ ብሎ ቤተሰቦቹን አታሎ ወደ ተባለበት ፀበል ሳይወስዳት ወደ አረብ ሃገር ተሰደው ምን እንደደረሰባቸው እንጃ እድላዊትም ከመጣች አንስታ ከአልጋ ላይ አልተነሳችም አሉ"፡፡
"ማን ነገረሽ ? እነሱ ቤት እንደማትደርሽ ነግረሽኝ ነበር"::
እድላዊት በጠና መታመሟን የነገረኝ ጉልላት ነው፡፡ እኔማ ከቤትም ስወጣ ሰው ሁሉ እንደ ዕብድ ውሻ ይሸሸኛል፡፡ አለች የፈላውን ቡና እየቀዳች፡፡
"ለዚሁ ሁሉ ስቃይና መከራ ያበቃሁሽ እኔ ነኝ፡፡ እንደበደልኩሽም አውቃለሁ፡፡ ግን ወድጀ አይደለም፡፡ የሃገር ጉዳይ ሆኖብኝ ነው፡፡ ጥየሽ የሔድኩት ፤ ብዙ አትፍረጅብኝ ሃገር ሰላም ካልሆነች እኛም ሰላም እንደማናገኝ አንችም ታውቂያለሽ" አለ ፤ ያሬድ፡፡
"እግዚአብሄር እንኳን ከእሳት አትርፎህ ለአይነ ስጋ እንድንገናኝ አበቃን እንጂ ያለፈው አልፏል፡፡ አሁንም አንተ ከመጣህ ጊዜው አይርቅም፡፡ የተደበቀው ሚስጢር ይውጣና እኔም እናቴ ናፍቃኛለች፡፡ ይሄው ካየኋት፤ አራት አመታትን ጨርሰን አምስተኛ አመታችንን ልንይዝ ነው፡፡ ምንም ቢሆን የእናት ክፉ የለውም፡፡ ባላወቀችው ነገር እንደጠላችኝ አውቃለሁ አለች፡፡ የቀሉ አይኖቿን እያሻሸች፡፡
እድላዊት በደረሰባት ጉዳት የተነሳ የአልጋ ቁራኛ ሆናለች፡፡ እህል እንኳን መቅመስ አቅቷታል፡፡
ተመስገን የቁም ስቃይና መከራ እያየ ባለበት ሰዓት ሞቷል እየተባለ የተወራለት ያሬድ መምጣቱን ሲሰማ
ወደ አረብ ሃገር ሲሰደድ ሶስት ሰዓት የፈጀበት የገመሪ ተራራ እፊቱ ላይ የተጋረጠበት ያክል መስሎ ተሰማው፡፡
ከአምስት ቀን እረፍት በኋላ፤ የተደበቀውን ሚስጢር ለማውጣት ይመለከታቸዋል የተባሉትን ዘመድና ሽማግሌዎች ለማነጋገር በጥዋት ተነሳ፡፡ የውጭ በሩን ከፍቶ ሳይወጣ ከቤቱ ማዶ ላይ አንድ ነጭ ጋቢ የለበሰ ሰው አየ፡፡ ወደ እሱ ቤት እየመጣ ይመስላል፡፡ ወደ አሰበበት መሄዱን ተወት አድርጎ ወደ እሱ የሚመጣውን መጠባበቅ ጀመረ፡፡
በጥዋት ጋቢያቸውን ተከናንበው ወደ ያሬድ ቤት የሚመጡት ቄስ አሻግሬ ነበሩ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ" ? አሉ ቄስ አሻግሬ፡፡ እስሩ ደርሰው፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደሩ ቄስ አሻግሬ"?፡፡
"እንኳን ለሃገርህ አበቃህ" ፡፡
ልጆች ደህና ናቸው ?፡፡
"ደህና ናቸው ፤ እንዲያው አንተ ለጤናህ ደህናነህ ?
ደህና ነኝ፡፡ ወደ ቤት ይግቡ ? ቄስ አሻግሬ አለ፡፡
አይ! አልገባም ቸኮል እላለሁ፡፡ እንዲያው በጥዋቱ ተነስተህ ኖሯል፡፡ የምትሄድበት አለ እንዴ ? አሉ፡፡
አዎ፤ የምሄድበት ነበረኝ፡፡ ከማዶ ስትመጡ ሳይ ጊዜ ነው፡፡ ወደ እኔ መምጣትዎን ሳውቅ የጠበኩዎት፡፡ ብሎ ምን ነው ደህና አይደሉም እንዴ? አለ፡፡
አይ! እኔስ ደህና ነኝ፡፡ እንዲያው እኒያ ቄስ መልካሙ ወደ አንተ ልከውኝ ነበር፡፡ የመጣሁት አሉ፡፡
ምን ነው በሰላም ነው? አለ ያሬድ፡፡ እድላዊት ምን ሆነች ብሎ እየተጠራጠረ፡፡
ልጁን ወይም ማሳደጊያ ይክፈለን እኛም አቅማችን እየደከመ ነው፡፡ እድላዊትም በሽተኛ ሆናለች፡፡ አንድ ነገር ያድርግልን ብለው ነው የላኩኝ አሉ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
ሚስጥሩ
ከአራት ዓመት ከውጊያ በኋላ፡፡ እንደ ማንኛውም የሰራዊት አባላት ዓመታዊ የወር ፍቃድ ደረሰው፡፡ የታጠቀውን የመንግስት መሳሪያ ለቅርብ አመራሩ አስረከበ፡፡ የፍቃድ ወረቀት ተቀበለ፡፡ የትግል አጋሮቹ ወደ ቤተሰቦቹ ሸኙት፡፡
የወርሃዊ ፍቃድ የተሰጠው እለት አራት አመታትን እንዳልቆየ ባለቤቱንና ልጁን ቶሎ ደርሶ ለማየት አንድ ቀን ሌሊት አልነጋ አለው፡፡ ካሳለፈው አራት ዓመታት በላይ በአይኑ ላይ እንቅልፍ የሚባል እንኳን ሳያልፍ ፍጥጥ ብሎ አነጋ፡፡ የሌሊቱ እንቅልፍ ወደ ቀን ተቀይሮበታል፡፡ ከመኪና ወንበር እያወዛወዘ ያላትመዋል፡፡
ያሬድ ከሁለት ቀን የመኪና ጉዞ በኋላ፤ አመሻሽ ላይ የትውልድ ቀየው ደረሰ፡፡ ሰፈሩ ሁሉ ዓዲስ ሆነበት፡፡ አካባቢው ተቀያይሯል፡፡ ተገረመ ፤ ከቤቱ አካባቢ
ዳገቱ ላይ ሻንጣውን አውርዶ አረፍ አለ፡፡ አይኖቹን በእሱ ቤት ላይ ተከላቸው፡፡ የእሱ ቤት ሰርቶት እንደሄደ አላገኘውም፡፡ የጣራው ሳር እረግፏል፡፡
የግቢውም አጥር ወላልቋል፡፡ በውስጡ ሰው ያለበት አይመስልም፡፡ ቤተሰቦቹን የሚያገኝ አልመስል አለው፡፡ ሆዱ በፍራት ተዋጠ፡፡ አይኖቹ በእንባ ተሞሉ፡፡ ወደ ወላለቀውና ፈራረሰው ቤቱ ተጠጋ፡፡
ከቤቱ ደጅ ላይ ሁለት ወንድ ህፃናት ልጆች እየቦረቁ ይጫወታሉ፡፡ አትኩሮ ተመለከታቸው፡፡ አንደኛው ህፃን ትልቅ እና ሰውነቱ ለወጥወጥ ቢልበትም የራሱ ልጅ ምትኩ እንደሆነ አልተጠራጠረም ነበር፡፡
ሁለተኛው ህፃን ግን የማን እንደሆነ ሊያውቀው አልቻለም፡፡ ወደ ሚጫወቱት ህፃናት ተጠግቶ ልጁን ምትክ ምትኩ? ብሎ ተጣራ፡፡ ህፃኖቹ የራስ የራሳቸውን እየተጨዋወቱ ከስራቸው ተጠግቶ የቆመውን ያሬድን አላዩትም ነበር፡፡ ህፃን ምትኩ መጫወቱን ትቶ ቀና አለ፡፡ በሰውነቱ ግዙፍ የሆነ ሰው አዬ፡፡ አባቱ እንደሆነ አያውቅም፡፡ ፈርቶ የወንድሙን የሁሉባንተን እጅ እየጎተተ ሸሽተው ወደ ቤት ገቡ፡፡
ምን ሁናችሁ ነው የምትሮጡት? ውሻ አባረራችሁ እንዴ ? አለች አበበች፡፡ ልጆቿ እየሮጡ ሲገቡ ደንግጣ፡፡
"ህፃን ምትኩ በተቆራረጠ ትንፋሽ ውሻ አይደለም ፤ መጥቷል" አላት፡፡
"የማን ሰው ነው የመጣው" ?፡፡
"አላውቀውም ሲያዩት ያስፈራል፡፡ ውጭና እይው እውጭ ቁሟል አላት፡፡ ውጭ ውጭውን እየተመለከተ፡፡
አበበች ውጭ እና እይው ሲላት የባሰ ድንጋጤ ጨመረባት፡፡ የሚያስፈራ ሰው ደግሞ ከየት መጣብኝ፡፡ እንዲያው አምላኬ ምን ልታሰማኝ ይሆን? ቤቴን ሰው አያውቀው፡፡ እንዲያው ሰርታ በላች ብለው ሊጨርሱኝ ይሆን? ከሰው ጋርም ባይሆን ከራሷ ጋር ያወራችው ነበር፡፡
ወደ ውጭ ብቅ አለች፡፡ እውነትም የሚያስፈራ ሰው ነው፡፡ የውጩን በር ከፍቶ ገባ፡፡ ሰውነቷ ተርበተበተ፡፡ የሚያስፈራው ሰውየ እየቀረባት መጣ፡፡
ለአራት አመታት የተለያት ባለቤቷ ያሬድ ነው፡፡ ማመን አቃታት፡፡ለመራመድ እግሮቿ ተሳሰሩ፡፡ አይኖቿ ያሬድ ላይ እንደተተከሉ በናፍቆት እንባ ተሞሉ፡፡
አበበች በደረሰባት ስቃይና መከራ ተጎሰቋቁላለች፡፡ የሃያ አምስት አመት ወጣት መምሰሏ ቀርቶ የአምሳ አመት አሮጊት ሆናለች፡፡ ያሬድ አዘነ፡፡ እያለቀሰ ተጠመጠመባት፡፡ ቤቱ ከሃዘን እንባ ወደ ደስታ እንባ ተቀየረ፡፡ አበበች የደረሰባትን ስቃይና መከራ እንዲሁም ባለቤቷ ያሬድ ከሄደ ስለወለደችው ልጅ ሁሉባንተ አጫውታው ልጁም የራሱ እንደሆነ ነግራው አምኖ ተቀብሏት ፡፡ ያሳለፉትን ናፍቆትና ትዝታ እያስታወሱ ሲለቃቀሱና ሲያወሩ ቢቆዩም ስለተደበቀው ሚስጢር ምንም ነገር ሳያወሩ አድረው በማግስቱ ጥዋት ነበር፡፡
ቡና ተፈልቶ "እንዴት አደረግሽው ያንን ነገር ያላት ?
"የቱን ነገር ? አለች ጥያቄው ግራ አጋብቷት፡፡
"ሚስጢሩን ነዋ አላት"፡፡
"አይ! ምነው ሁሉንም ነገር ለማንም እንዳትነግሪ ብለኸኝ በባዶ ቤት ያለቤተሰብና ያለ ዘመድ አዳፍነህብኝ ሄደህ ፤ እንዴት ነው ሚስጢሩ የሚወጣው?፡፡ ይኸው ከዛን እለት ጀምሮ ተመስገን እኔ ደጀም አልደረሰም፡፡ እስካሁንም አላየሁት፡፡ ብላ የነበረውን ሁኔታ ስታነሳሳ ውስጧ ተረበሸ፡፡ የብሶት እንባ አለቀሰች፡፡
ያሬድ የሚለው የሚናገረውን ቢያጣ ግራ ቢገባውም፡፡ ከተመስገን ያልተገናኛችሁት እዚሁ እያለ ነው ወይስ ከሃገር ለቆ ነው? አለ፡፡
በፊቷ ላይ የሚወርደውን እንባ በፎጣዋ ጠረግ ጠረግ እያደረገች "እዚሁ እያለ ሲሸሸኝ ፣ ሲሸሸኝ ቆይቶ እህቱን እድላዊትን ወደ ፀበል ልወስዳት ነው፡፡ ብሎ ቤተሰቦቹን አታሎ ወደ ተባለበት ፀበል ሳይወስዳት ወደ አረብ ሃገር ተሰደው ምን እንደደረሰባቸው እንጃ እድላዊትም ከመጣች አንስታ ከአልጋ ላይ አልተነሳችም አሉ"፡፡
"ማን ነገረሽ ? እነሱ ቤት እንደማትደርሽ ነግረሽኝ ነበር"::
እድላዊት በጠና መታመሟን የነገረኝ ጉልላት ነው፡፡ እኔማ ከቤትም ስወጣ ሰው ሁሉ እንደ ዕብድ ውሻ ይሸሸኛል፡፡ አለች የፈላውን ቡና እየቀዳች፡፡
"ለዚሁ ሁሉ ስቃይና መከራ ያበቃሁሽ እኔ ነኝ፡፡ እንደበደልኩሽም አውቃለሁ፡፡ ግን ወድጀ አይደለም፡፡ የሃገር ጉዳይ ሆኖብኝ ነው፡፡ ጥየሽ የሔድኩት ፤ ብዙ አትፍረጅብኝ ሃገር ሰላም ካልሆነች እኛም ሰላም እንደማናገኝ አንችም ታውቂያለሽ" አለ ፤ ያሬድ፡፡
"እግዚአብሄር እንኳን ከእሳት አትርፎህ ለአይነ ስጋ እንድንገናኝ አበቃን እንጂ ያለፈው አልፏል፡፡ አሁንም አንተ ከመጣህ ጊዜው አይርቅም፡፡ የተደበቀው ሚስጢር ይውጣና እኔም እናቴ ናፍቃኛለች፡፡ ይሄው ካየኋት፤ አራት አመታትን ጨርሰን አምስተኛ አመታችንን ልንይዝ ነው፡፡ ምንም ቢሆን የእናት ክፉ የለውም፡፡ ባላወቀችው ነገር እንደጠላችኝ አውቃለሁ አለች፡፡ የቀሉ አይኖቿን እያሻሸች፡፡
እድላዊት በደረሰባት ጉዳት የተነሳ የአልጋ ቁራኛ ሆናለች፡፡ እህል እንኳን መቅመስ አቅቷታል፡፡
ተመስገን የቁም ስቃይና መከራ እያየ ባለበት ሰዓት ሞቷል እየተባለ የተወራለት ያሬድ መምጣቱን ሲሰማ
ወደ አረብ ሃገር ሲሰደድ ሶስት ሰዓት የፈጀበት የገመሪ ተራራ እፊቱ ላይ የተጋረጠበት ያክል መስሎ ተሰማው፡፡
ከአምስት ቀን እረፍት በኋላ፤ የተደበቀውን ሚስጢር ለማውጣት ይመለከታቸዋል የተባሉትን ዘመድና ሽማግሌዎች ለማነጋገር በጥዋት ተነሳ፡፡ የውጭ በሩን ከፍቶ ሳይወጣ ከቤቱ ማዶ ላይ አንድ ነጭ ጋቢ የለበሰ ሰው አየ፡፡ ወደ እሱ ቤት እየመጣ ይመስላል፡፡ ወደ አሰበበት መሄዱን ተወት አድርጎ ወደ እሱ የሚመጣውን መጠባበቅ ጀመረ፡፡
በጥዋት ጋቢያቸውን ተከናንበው ወደ ያሬድ ቤት የሚመጡት ቄስ አሻግሬ ነበሩ፡፡
"ደህና አደርህ ያሬድ" ? አሉ ቄስ አሻግሬ፡፡ እስሩ ደርሰው፡፡
"እግዚአብሔር ይመስገን ደህና አደሩ ቄስ አሻግሬ"?፡፡
"እንኳን ለሃገርህ አበቃህ" ፡፡
ልጆች ደህና ናቸው ?፡፡
"ደህና ናቸው ፤ እንዲያው አንተ ለጤናህ ደህናነህ ?
ደህና ነኝ፡፡ ወደ ቤት ይግቡ ? ቄስ አሻግሬ አለ፡፡
አይ! አልገባም ቸኮል እላለሁ፡፡ እንዲያው በጥዋቱ ተነስተህ ኖሯል፡፡ የምትሄድበት አለ እንዴ ? አሉ፡፡
አዎ፤ የምሄድበት ነበረኝ፡፡ ከማዶ ስትመጡ ሳይ ጊዜ ነው፡፡ ወደ እኔ መምጣትዎን ሳውቅ የጠበኩዎት፡፡ ብሎ ምን ነው ደህና አይደሉም እንዴ? አለ፡፡
አይ! እኔስ ደህና ነኝ፡፡ እንዲያው እኒያ ቄስ መልካሙ ወደ አንተ ልከውኝ ነበር፡፡ የመጣሁት አሉ፡፡
ምን ነው በሰላም ነው? አለ ያሬድ፡፡ እድላዊት ምን ሆነች ብሎ እየተጠራጠረ፡፡
ልጁን ወይም ማሳደጊያ ይክፈለን እኛም አቅማችን እየደከመ ነው፡፡ እድላዊትም በሽተኛ ሆናለች፡፡ አንድ ነገር ያድርግልን ብለው ነው የላኩኝ አሉ፡፡
👍44❤2🎉2