#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ካርተር በርክሌ ውድ ሽሚዙን በደንብ ማኒኩየር በተሰራው ጣቶቹ በደንብ አድርጎ አስተካከለው:: የዶክተር ሮበርትስ
ታካሚ የሆነው የኢንቨስትመንት ባንከሩ ካርተር በርክሌ ሁሉ ነገሩ ውዷ ነው፡፡ ምርጥ መኖሪያ ቤት፣ ምርጥ ምርጥ የቪንቴጅ ጃንዋር ስፖርት መኪኖች እና ሁሉም ቁጭ ያሉበት በምርጥ ሁኔታ ፈርኒሽድ የተደረገው የቤት ውስጥ ቢሮው እራሱ በጣም ውድ ነው፡፡ እንኳን እቃዎቹ ሲያወራ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ሁሉ በጣም የተመረጡ ናቸው፡፡
እዚህ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እያወሩ እያሉ ካርተር ትላንትና ማታ መኝታ ቤቱ ውስጥ የሆነ ሰው ሊያስፈራራው በማሰብ የሞተ አይጥ አስቀምጦ እንደነበር እየነገረው ነበር። የሞተ አይጥን ማስቀመጣቸው የማፍያዎች ማስፈራሪያ ስልት እንደሆነ ጭምር እያስረዳው ነበር፡፡
“ይሄን ነገር ያደረጉት በእርግጥም እኔን ሊያስፈራሩ አስበው ነው፡፡ደግሞም ተሳክቶላቸዋል። ባይገርምህ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን እናንተ ወደ እኔ ባትመጡ እንኳን እኔ እራሴ ጉዳዩን ለማመልከት ወደ እናንተ መምጣቴ አይቀርም ነበር።
ጆንሰንም ራሱን በአዎንታ በመነቅነቅ የቤቱን ዙሪያ ሲመለከት ዕቃዎቹ
በደንብ ከመወልወልም በላይ የመፅሀፍ መደርደሪያው ሼልፍም ራስን
በመገንባት ላይ እና በፋይናንስ ዙሪያ በተፃፉ መፅሀፍት በሥርዓት
ተጠቅጥቀዋል። አሁን ላይ ካርተር በርክሌይን እየተመለከተው ያለው ጆንሰን
ዶክተር ሮበርትስ ስለ ካርተር ከማስታወሻዋ ላይ ከፃፈችው ነገር ጋር
በመስማማቱ ተናደደ፡፡
ጆንሰን ካርተርን አስመልክታ ኒኪ የፃፈችውን ሲያነብ “መቀወሱ
ያልተረጋገጠ በከንቱ ስሜት ውስጥ የሚናውዝ የሜክሲኮ ወንጀለኞች
ሊገድሉት እንደሚያሳድዱት የሚናገር (ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የሌለው)
ለረዥም ጊዜ በጭንቀት ውስጥ የኖረ። ምናልባት በልጅነቱ በደረሰበት ስቃይ
ምክንያት ሊሆን ይችላል? (ወይንም ደግሞ ሜክሲኮ ውስጥ በጉርምስናው
ዘመን ኖሯልና ምናልባት እዚያ የሆነ ነገር ተከስቶ ይሆን?) ውስጡ ያላደገ
ቋሚ የሆነ ፆታዊ ግንኙነት የሌለው እና በግንኙነት አብረውት ያሉ ሰዎችንም በጣም አድርጎ የሚቆጣጠር ነው።” ይላል ማስታወሻው፡፡
ዶክተር ሮበርትስ ካርተር በርክሌን የገለፀችበት መንገድ በሙሉ የተቀበለው ቢሆንም አንድ ነገር ረስታለች እሱም “የሰዎች አትኩሮትን (ታይታን) የሚፈልግ ባህሪ ያለው መሆኑ ነው። ይህንን ደግሞ በእሱ ላይ ያላየችው እሷም የዚህ ልክፍት ስላለባት ነው ብሎ አሰበ፡፡ ለዚህም ነው
ካርተር ከዚህ በፊት በተካሄዱት ግድያዎች ውስጥ ዋነኛ ተፈላጊ ሰው መሆኑን ለማሳየት ያጫወተውን የአይጥ ታሪክ ፈጥሮ ለጆንሰን የተናገረው።
ይሄ ቀሽም ሰው ራሱን እንደተፈላጊ ሰው ያያል ወይንም ደግሞ የሆነ እሱ ስለግድያው የሚያውቀውን ነገር እንዳላውጣጣው እያዘናጋኝ ነው
ብሎም አሰበ፡፡
“ቤትህ ውስጥ ጠባቂዎች አሉህ መሰለኝ?” ብሎ ቅድም ወደ ቤቱ ሲገባ
የተመለከታቸውን ብዙም ስልጠና እንደሌላቸው የሚያስታውቁትን የጥበቃ
ሰዎቹን አልፎ እንደገባ አስታውሶ ካርተርን ጠየቀው። ቤቱ ውስጥ ሲገባ ከጠባቂዎቹ ሌላም የሲ.ሲ.ቲቪ
ካሜራዎችንም አይቶዐካሜራዎችንም በየቦታው ገጥመሃል አይደል እንዴ?”
“አዎን ቤቱ ጥበቃ ስለሚያስፈልገው በጠባቂዎችም፣ በካሜራም ነው
የሚጠበቀው። ግን ዋናው መኝታ ቤቴ ውስጥ ካሜራ አልገጠምኩኝም” ብሎ
መለሰለት፡፡
ጆንሰንም “ለምን ዋናው መኝታ ቤትህ ውስጥ ካሜራ አላስገጠምክም?
ብሎ ጠየቀው፡፡
ባንከሩም እንዴት ይሄ አይገባህም በሚል ሀሳብ ይመስል የጎረምሳ ፈገግታ ከለገሰው በኋላ “እዚህ ጋር የተማረ ሰው ግምት ይኖርሃል ብዬ አስባለሁ። ጠባቂዎቼ ከሁሉም ካሜራዎች በቀጥታ መረጃዎች ይደርሳቸዋል።እኔ ደግሞ በግሌ የማደርጋቸውን ነገሮች ማንም እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። ለዚያም ስል ነው በዋናው መኝታ ክፍሌ ውስጥ ካሜራ ያላስገጠምኩት፡፡ በሁሉም ወደ ቤቴ በሚያስገቡ በሮች ላይ ካሜራ
ተገጥሞባቸዋል። እሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ፎቅ ላይም ካሜራዎችን
አስገጥሜያለሁ። ስለ እዚህ ወደ እዚህ ቤት የሚገባም ሆነ የሚወጣ ሰው
በካሜራው መታየት ይችላል” ብሎ መለሰ፡፡
“መልካም” አለና ጆንሰን በመቀጠልም “የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ
ተቀምጦ ካገኘህ በኋላ መቼስ ካሜራዎቹ የቀረፁትን ቪዲዩዎች ተመልክተሀቸዋል አይደል?” ብሎ ጠየቀው፡፡
“አዎን አይቻቸዋለሁ”
“ግን ማንም ሰው አላየህም?”
ቤቴ ውስጥ ከሚሰሩ ሰዎች በስተቀር አንድም ሰውን አላየሁም። ይሄ ታዲያ አይገርምም?” ብሎ የሸሚዙን ኮሌታ በሀይል ጎተተው።
“እና እንዴት ነው ይሄ አንተ የማፍያዎች የማስፈራሪያ መንገድ ነው ብለህ ያሰብከውን የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ ድረስ ሊያስቀምጡ የቻሉት?” ብሎ ጆንሰን ጠየቀ፡፡
ካርተርም ፊቱ ላይ ግራ የመጋባት ፊት እያሳየው “እኔ ይሄንን በምን አውቃለሁ? መርማሪ ፖሊሱ እንግዲህ አንተ ነህ አይደል? አንተው ንገረኝ
እንጂ” ብሎ መለስ፡፡
“እና ቪድዮው ላይ አዲስ ሰው እስካላየህ ድረስ ቤት ውስጥ የሚሰራ
ሰው ነው አይጡን መኝታ ቤትህ ያስቀመጠው ማለት ነው፡፡ አይመስልህም?”ብሎ ጠየቀው እኔ ጋር አለ ብሎ ባልጠበቀው የራሱ ትዕግስት ጭምር እየተገረመ፡፡
“ይሄማ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኔ እነዚህን ሰዎች ስቀጥር
የበፊት ህይወታቸውን በሚገባ አስጠንቼ እና ተጠንቅቄ ነው፡፡ ስለሆነም
አሁን አንተ የተናገርከው ነገር ሊሆን አይችልም...”
ብሎ ያሰበውን ነገር ተናግሮ ሳይጨርስ ጆንሰን አቋረጠው እና ምናልባት አይጡን ልታሳየኝ ትችላለህ? ስለዚህ አይጡን አንስቼ ምርመራ እንዲደረግበት ማድረግ እችላለሁ” አለው ከወንበሩ ላይ ተነሳ፡፡
“አይጡን ላሳይህ አልችልም” ብሎ መለሰለት፡፡ ጆንሰንም የካርተርን
መልስ ሲሰማ ዶክተር ሮበርትስ “ዝም ብሎ የቅዠት ሀሳብ የሚፈጥር ብላ
የተናገረችው ነገር ትክክል እንደሆነ አወቀ።
ለምንድነው አይጡን የማታሳየኝ?” ብሎ ኮስተር ብሎ ጠየቀው እና ለእንደዚህ አይነት ሰው ዶክተር ሮበርትስ እንዴት በየቀኑ የቴራፒስት ህክምና ልትሰጥ እንደምትችል ራሱን ጠየቀ፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ቴራፒስቶች አፍንጫቸው መመታት የለበትም ታዲያ?
“ትላንትና ማታ ነው አይጡን ያገኘሁት እሱን ደግሞ ነግሬሀለሁ አይደል?” ብሎ ካርተር ክርክሩን በመቀጠል “ቤቴን የምታፀዳው ሴት ደግሞ እስከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ድረስ አልመጣችም ነበር፡፡ እሷ እስክትመጣ ድረስ ደግሞ አይጡን ክፍሌ ውስጥ ልተወው አልችልም፡፡ ምክንያቱም አይጡ ምን አይነት በሽታ ይዞ እንደመጣ ማንም አያውቅም፡፡” ብሎ መለሰለት።
“እና መረጃ የሚሆነንን ነገር ነው የጣልከው?”
“መጣል ነበረብኝ”
“አይጡን ከክፍልህ ስታስወግድ ያየህ ሰው አለ?”
የለም ያው እንዳልኩህ በጣም መሽቶ ነበር” ብሎ ሲመልስለት የጆንሰን
ትዕግስት ተሟጥጦ ስላለቀ አሁንም ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነሳ፡፡
የታለ ቆሻሻ የምትጥልበት የቆሻሻ ማስቀመጫህ? ምናልባት አይጡ
እዚያው ቆሻሻ መጣያው ውስጥ ይኖር ይሆናል ይሄኔ” አለው ጆንሰን
ይህንን የጆንሰን ጥያቄ ሲሰማ ቢያንስ ካርተር ማፈር ነበረበት፤ ግን እሱ
ይበልጥ ድርቅ ብሎ “አሁን ላይ በእርግጠኝነት ባዶ ነው የሚሆኑት። ቆሻሻ የሚሰበስቡ ሰዎች ዛሬ በጠዋት ነው ያለወትሮ የመጡት። ያንን አስቢ
አይጡን ሌላ ቦታ ማስቀመጥ ነበረብኝ፡፡ ወይም በጣም ነው ያጠፋሁት.”ጆንሰን ወደ ዋናው የፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ለመመለስ መኪናውን በተጨናነቀ መንገድ ላይ ሲያሽከረክር ከአንድ ሰዓት በላይ ፈጅቶበታል ጣቢያውም የደረሰው በሚያስጠላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ካርተር በርክሌ ውድ ሽሚዙን በደንብ ማኒኩየር በተሰራው ጣቶቹ በደንብ አድርጎ አስተካከለው:: የዶክተር ሮበርትስ
ታካሚ የሆነው የኢንቨስትመንት ባንከሩ ካርተር በርክሌ ሁሉ ነገሩ ውዷ ነው፡፡ ምርጥ መኖሪያ ቤት፣ ምርጥ ምርጥ የቪንቴጅ ጃንዋር ስፖርት መኪኖች እና ሁሉም ቁጭ ያሉበት በምርጥ ሁኔታ ፈርኒሽድ የተደረገው የቤት ውስጥ ቢሮው እራሱ በጣም ውድ ነው፡፡ እንኳን እቃዎቹ ሲያወራ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ሁሉ በጣም የተመረጡ ናቸው፡፡
እዚህ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እያወሩ እያሉ ካርተር ትላንትና ማታ መኝታ ቤቱ ውስጥ የሆነ ሰው ሊያስፈራራው በማሰብ የሞተ አይጥ አስቀምጦ እንደነበር እየነገረው ነበር። የሞተ አይጥን ማስቀመጣቸው የማፍያዎች ማስፈራሪያ ስልት እንደሆነ ጭምር እያስረዳው ነበር፡፡
“ይሄን ነገር ያደረጉት በእርግጥም እኔን ሊያስፈራሩ አስበው ነው፡፡ደግሞም ተሳክቶላቸዋል። ባይገርምህ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን እናንተ ወደ እኔ ባትመጡ እንኳን እኔ እራሴ ጉዳዩን ለማመልከት ወደ እናንተ መምጣቴ አይቀርም ነበር።
ጆንሰንም ራሱን በአዎንታ በመነቅነቅ የቤቱን ዙሪያ ሲመለከት ዕቃዎቹ
በደንብ ከመወልወልም በላይ የመፅሀፍ መደርደሪያው ሼልፍም ራስን
በመገንባት ላይ እና በፋይናንስ ዙሪያ በተፃፉ መፅሀፍት በሥርዓት
ተጠቅጥቀዋል። አሁን ላይ ካርተር በርክሌይን እየተመለከተው ያለው ጆንሰን
ዶክተር ሮበርትስ ስለ ካርተር ከማስታወሻዋ ላይ ከፃፈችው ነገር ጋር
በመስማማቱ ተናደደ፡፡
ጆንሰን ካርተርን አስመልክታ ኒኪ የፃፈችውን ሲያነብ “መቀወሱ
ያልተረጋገጠ በከንቱ ስሜት ውስጥ የሚናውዝ የሜክሲኮ ወንጀለኞች
ሊገድሉት እንደሚያሳድዱት የሚናገር (ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የሌለው)
ለረዥም ጊዜ በጭንቀት ውስጥ የኖረ። ምናልባት በልጅነቱ በደረሰበት ስቃይ
ምክንያት ሊሆን ይችላል? (ወይንም ደግሞ ሜክሲኮ ውስጥ በጉርምስናው
ዘመን ኖሯልና ምናልባት እዚያ የሆነ ነገር ተከስቶ ይሆን?) ውስጡ ያላደገ
ቋሚ የሆነ ፆታዊ ግንኙነት የሌለው እና በግንኙነት አብረውት ያሉ ሰዎችንም በጣም አድርጎ የሚቆጣጠር ነው።” ይላል ማስታወሻው፡፡
ዶክተር ሮበርትስ ካርተር በርክሌን የገለፀችበት መንገድ በሙሉ የተቀበለው ቢሆንም አንድ ነገር ረስታለች እሱም “የሰዎች አትኩሮትን (ታይታን) የሚፈልግ ባህሪ ያለው መሆኑ ነው። ይህንን ደግሞ በእሱ ላይ ያላየችው እሷም የዚህ ልክፍት ስላለባት ነው ብሎ አሰበ፡፡ ለዚህም ነው
ካርተር ከዚህ በፊት በተካሄዱት ግድያዎች ውስጥ ዋነኛ ተፈላጊ ሰው መሆኑን ለማሳየት ያጫወተውን የአይጥ ታሪክ ፈጥሮ ለጆንሰን የተናገረው።
ይሄ ቀሽም ሰው ራሱን እንደተፈላጊ ሰው ያያል ወይንም ደግሞ የሆነ እሱ ስለግድያው የሚያውቀውን ነገር እንዳላውጣጣው እያዘናጋኝ ነው
ብሎም አሰበ፡፡
“ቤትህ ውስጥ ጠባቂዎች አሉህ መሰለኝ?” ብሎ ቅድም ወደ ቤቱ ሲገባ
የተመለከታቸውን ብዙም ስልጠና እንደሌላቸው የሚያስታውቁትን የጥበቃ
ሰዎቹን አልፎ እንደገባ አስታውሶ ካርተርን ጠየቀው። ቤቱ ውስጥ ሲገባ ከጠባቂዎቹ ሌላም የሲ.ሲ.ቲቪ
ካሜራዎችንም አይቶዐካሜራዎችንም በየቦታው ገጥመሃል አይደል እንዴ?”
“አዎን ቤቱ ጥበቃ ስለሚያስፈልገው በጠባቂዎችም፣ በካሜራም ነው
የሚጠበቀው። ግን ዋናው መኝታ ቤቴ ውስጥ ካሜራ አልገጠምኩኝም” ብሎ
መለሰለት፡፡
ጆንሰንም “ለምን ዋናው መኝታ ቤትህ ውስጥ ካሜራ አላስገጠምክም?
ብሎ ጠየቀው፡፡
ባንከሩም እንዴት ይሄ አይገባህም በሚል ሀሳብ ይመስል የጎረምሳ ፈገግታ ከለገሰው በኋላ “እዚህ ጋር የተማረ ሰው ግምት ይኖርሃል ብዬ አስባለሁ። ጠባቂዎቼ ከሁሉም ካሜራዎች በቀጥታ መረጃዎች ይደርሳቸዋል።እኔ ደግሞ በግሌ የማደርጋቸውን ነገሮች ማንም እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። ለዚያም ስል ነው በዋናው መኝታ ክፍሌ ውስጥ ካሜራ ያላስገጠምኩት፡፡ በሁሉም ወደ ቤቴ በሚያስገቡ በሮች ላይ ካሜራ
ተገጥሞባቸዋል። እሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ፎቅ ላይም ካሜራዎችን
አስገጥሜያለሁ። ስለ እዚህ ወደ እዚህ ቤት የሚገባም ሆነ የሚወጣ ሰው
በካሜራው መታየት ይችላል” ብሎ መለሰ፡፡
“መልካም” አለና ጆንሰን በመቀጠልም “የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ
ተቀምጦ ካገኘህ በኋላ መቼስ ካሜራዎቹ የቀረፁትን ቪዲዩዎች ተመልክተሀቸዋል አይደል?” ብሎ ጠየቀው፡፡
“አዎን አይቻቸዋለሁ”
“ግን ማንም ሰው አላየህም?”
ቤቴ ውስጥ ከሚሰሩ ሰዎች በስተቀር አንድም ሰውን አላየሁም። ይሄ ታዲያ አይገርምም?” ብሎ የሸሚዙን ኮሌታ በሀይል ጎተተው።
“እና እንዴት ነው ይሄ አንተ የማፍያዎች የማስፈራሪያ መንገድ ነው ብለህ ያሰብከውን የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ ድረስ ሊያስቀምጡ የቻሉት?” ብሎ ጆንሰን ጠየቀ፡፡
ካርተርም ፊቱ ላይ ግራ የመጋባት ፊት እያሳየው “እኔ ይሄንን በምን አውቃለሁ? መርማሪ ፖሊሱ እንግዲህ አንተ ነህ አይደል? አንተው ንገረኝ
እንጂ” ብሎ መለስ፡፡
“እና ቪድዮው ላይ አዲስ ሰው እስካላየህ ድረስ ቤት ውስጥ የሚሰራ
ሰው ነው አይጡን መኝታ ቤትህ ያስቀመጠው ማለት ነው፡፡ አይመስልህም?”ብሎ ጠየቀው እኔ ጋር አለ ብሎ ባልጠበቀው የራሱ ትዕግስት ጭምር እየተገረመ፡፡
“ይሄማ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኔ እነዚህን ሰዎች ስቀጥር
የበፊት ህይወታቸውን በሚገባ አስጠንቼ እና ተጠንቅቄ ነው፡፡ ስለሆነም
አሁን አንተ የተናገርከው ነገር ሊሆን አይችልም...”
ብሎ ያሰበውን ነገር ተናግሮ ሳይጨርስ ጆንሰን አቋረጠው እና ምናልባት አይጡን ልታሳየኝ ትችላለህ? ስለዚህ አይጡን አንስቼ ምርመራ እንዲደረግበት ማድረግ እችላለሁ” አለው ከወንበሩ ላይ ተነሳ፡፡
“አይጡን ላሳይህ አልችልም” ብሎ መለሰለት፡፡ ጆንሰንም የካርተርን
መልስ ሲሰማ ዶክተር ሮበርትስ “ዝም ብሎ የቅዠት ሀሳብ የሚፈጥር ብላ
የተናገረችው ነገር ትክክል እንደሆነ አወቀ።
ለምንድነው አይጡን የማታሳየኝ?” ብሎ ኮስተር ብሎ ጠየቀው እና ለእንደዚህ አይነት ሰው ዶክተር ሮበርትስ እንዴት በየቀኑ የቴራፒስት ህክምና ልትሰጥ እንደምትችል ራሱን ጠየቀ፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ቴራፒስቶች አፍንጫቸው መመታት የለበትም ታዲያ?
“ትላንትና ማታ ነው አይጡን ያገኘሁት እሱን ደግሞ ነግሬሀለሁ አይደል?” ብሎ ካርተር ክርክሩን በመቀጠል “ቤቴን የምታፀዳው ሴት ደግሞ እስከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ድረስ አልመጣችም ነበር፡፡ እሷ እስክትመጣ ድረስ ደግሞ አይጡን ክፍሌ ውስጥ ልተወው አልችልም፡፡ ምክንያቱም አይጡ ምን አይነት በሽታ ይዞ እንደመጣ ማንም አያውቅም፡፡” ብሎ መለሰለት።
“እና መረጃ የሚሆነንን ነገር ነው የጣልከው?”
“መጣል ነበረብኝ”
“አይጡን ከክፍልህ ስታስወግድ ያየህ ሰው አለ?”
የለም ያው እንዳልኩህ በጣም መሽቶ ነበር” ብሎ ሲመልስለት የጆንሰን
ትዕግስት ተሟጥጦ ስላለቀ አሁንም ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነሳ፡፡
የታለ ቆሻሻ የምትጥልበት የቆሻሻ ማስቀመጫህ? ምናልባት አይጡ
እዚያው ቆሻሻ መጣያው ውስጥ ይኖር ይሆናል ይሄኔ” አለው ጆንሰን
ይህንን የጆንሰን ጥያቄ ሲሰማ ቢያንስ ካርተር ማፈር ነበረበት፤ ግን እሱ
ይበልጥ ድርቅ ብሎ “አሁን ላይ በእርግጠኝነት ባዶ ነው የሚሆኑት። ቆሻሻ የሚሰበስቡ ሰዎች ዛሬ በጠዋት ነው ያለወትሮ የመጡት። ያንን አስቢ
አይጡን ሌላ ቦታ ማስቀመጥ ነበረብኝ፡፡ ወይም በጣም ነው ያጠፋሁት.”ጆንሰን ወደ ዋናው የፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ለመመለስ መኪናውን በተጨናነቀ መንገድ ላይ ሲያሽከረክር ከአንድ ሰዓት በላይ ፈጅቶበታል ጣቢያውም የደረሰው በሚያስጠላ
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....የውስጤን ሥቃይና የሕሊናዬን ሰፊ ጠባሳ ጠልቀው ያላዩ የቅርብ
ዘመዶቻችን «ዛሬማ ተበላሽቶ፣ የሱ ነገር እንዲህ ሆኖ ቀረ፡፡ ያየህይራድን የመሰለ
አንበሳ አባት እያለው ወግ ማዕረግ ያለማየቱ...» እያሉ ያጉመተምታሉ፡፡ ከቤት
ውጪ ማደሬ ያለ ማቋረጥ በመዘውተሩ ሁኔታውን መላው ቤተሰብ ከዳር እስከ
ዳር ዐወቀ፡፡ ደግማ ደጋግማ እናቴ እያፈረች፣ እኅቴ በተለይም የእናቴ
ምስጢረኛና የቅርብ ጓደኛ ወይዘሮ አማረች መኝታ ቤት ድረስ እየገቡ፣ ተው
ደግም አይደል የትልቅ ሰውና የጨዋ ልጅ እንዲህ አይደለም፡፡ እናትህ ብታለቅስ
ታደርስብሃለች» እያሉ ለወጉ ያህል ገሠጹኝ፡፡
እኔን የምመክራትና የምዳኛት ወደ ፊትም ሆነ ወደ ኋላ የማስኪዳት እኔው ራሴ ብቻ በመሆኔ የእነርሱን ምክር ሁሉ እንደሚያልፍ የበረዶ ውሽንፍር
ቆጠርኩት። በጠቅላላ መጻሕፍቶቼንና ልብሶቼን ውስጥ ውስጡን አንድ በአንድ
እግዥ ጨረስኩ፡፡ ከሁለትና ከሦስት ቀን አዳር በኋላ ወደ ወላጆቼ ቤት ስገባ ዘና
ብሎ የሚያናግረኝ ሰው አልነበረም፡፡
አባቴም ከቤት ውጪ በተደጋጋሚ ማደሬንና እንደ እናቴም አባባል «መዛተሌን» ቀስ በቀስ ሰማ።
«አግባ! ትዳር ንብረት ያዝ፣ እንደ ማንም የባለጌ ልጅ ሰፈር ለሰፈር
እትልከስከስ፣ ጎጆ ያስከብራል፣ ትዳር ግርማ ሞገስ ነው ያልኩህ ለዚህ ብዬ ነበር፡፡ያለበለዚያ ግን አካለ መጠን ከደረሰ ጐረምሳ ጋር ምን ያታግለኛል» ብሎ
ከነከተቴው ችላ አለኝ፡፡
ዋል አደር ብሎም «አደጋ ብቻ እንዳያገኘው እንጂ ልቡ መለስ
ሲልለትና ያበጠው ልቡ ሲሟሽሽ እንዳረጀች ውሻ ክትት ይላል» አለና ይብሱኑ ስለ እኔ የነበረውን 'አለና የለም ወይ?” እርግፍ አድርጎ ተወ፡፡
የሐሳቤ ተፃራሪ የሆነው አባቴ እንደ አህያ ሬሳ ቢጠላኝም ቅር አላለኝ፡፡ እኔ ግን «ይህ ነው ለሰው ልጅ የሚሰጠው ታላቅ የመኖር ጸጋ ብዬ ከጥላቻው ውስጥ ብርታትና እፎይታ የተሸለምኩ መሰለኝ።
ወደ ወላጆቼ ቤት ባሰኘን ጊዜ ገብቼ ባስፈለገኝ ሰዓት ውልቅ ማለት
ለመድኩ፡፡ እንደ ምኞቴ ሳልዘጋጅና ሳላስበው፣ የኑሮዬንም አዝማሚያ በሚገባ ሳላቅድ ድንገት ባለትዳር በመሆኔ ኑሮ በመጠኑ ተደናገረኝ። ሆኖም ትዳራችን የተመሠረተው በጽኑ ፍቅር ላይ በመሆኑ ፍላጎቴና ጉጉቴ ሁሉ ነጋ ጠባ
ለመሻሻልና አስደሳች ለውጥ ለማግኘት ሆነ። ወትሮ በቀላሉ ደንግጦ ይበረግግ
የነበረው አእምሮዬ የድፍረትና የወኔ ካፈያ ተርከፈከፈበት።
የየወዲያነሽን ቀኝ እጅ ያዝ አደርግና «ዛሬ ምን ያስፈልገናል?» ስላት ዐይን ዐይኔን እያየች እና የኮቴን አዝራሮች በጣቶቿ እየጠራረገች «ካለህማ....ያህል ይበቃኛል» ብላ ገንዘብ ስትጠይቀኝ የትዳርን አያያዝና አመራር ቀስ በቀስ
ለመድነው። በየወዲያነሽ በኩል የተቸገርኩበት ጉዳይ ቢኖር፡ ስትተኛም ይሁን ስትነሣ ስትበላም ይሁን ስትጠጣ አረ ተው ጌታነህ፡ ኧረ ተው! እረ ተው
ልጄን አሳየኝ? ሞቶም እንደሆነ ቁርጡን ንገረኝ ባይኖር ነው እንጂ ቢኖርግ
መቼ እንዲህ ዝም ትለኝ ነበር?» እያለች ስለምትጨቀጭቀኝ ነበር፡፡ ምንም እንኳ
አንዳንድ ነገርን አገላብጠው የማያዩ ቀባጣሪዎች «ጨካኝ አረመኔ ነች» እያሉ
እንደሚያሟትና ወደ ፊትም እንደሚያባጥሏት እያሰብኩ ለጊዜው ብበሳጭም እኔ ከማንም ይበልጥ የእኔዋን እና ቅኗን የወዲያነሽን አሳምሬ ስለማውቃት አባባላቸው ሁሉ ከወሬ እንኳ የነፈሰበት ተራ ወሬ ነው ብዬ እንደ ቤት ጉድፍ ጠራርጌ ጣልኩት።
ያን በማሕፀኗ ዘጠኝ ወር ሙሉ ተሽክማ በስንት የኑሮ ሥቃይ እና ውጣ ውረድ የወለደችውን ልጅዋንና አካሏን ለማየት እያለቀሰች ብታስቸግረኝም
የእናትነት ወጓ በመሆኑ ምንም ቅር አላለኝም፡፡
አንድ ቀን እሑድ ጥዋት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን ሳላስበውና
የሚያጋጥመኝን ሳልጠራጠር ከኪሴ እንድ ትንሽ ሰማያዊ ማኅደር አወጣሁ፡፡
በውስጡ የነበሩትን ልዩ ልዩ ሥዕሎች ተራ በተራ ስመለከት የወዲያነሽም
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል አድርጋ ትመለከት ነበር፡፡ የልጃችንን ሥዕል ኣየት
እንዳደረገች «ይኸውና» ብላ ባስደንጋጭ ሁኔታ ጮኸች፡፡ ከእጄ ላይ መንጭቃ
ደረቷ ላይ ለጠፈችው።
እነዚያ በእንባ ተኮትኩተው ያደጉት ዐይኖቿ የእንባ ኩልልታ እንጠፈጠፉ፡፡ ሥዕሉን ጠረጴዛው ላይ ወርውራ እግሬ ላይ ዘፍ አለች፡፡ እግሬን ባላት ጠቅላላ ኃይል ቁልቁል ጨምድዳ ስለ ያዘችው ጎትቼ ማላቀቅ አቃተኝ።
«ብዙ ሥቃይና መከራ ያየሁበት፣ ተንገላትቼ የተንከራተትኩበት የበኸር
ልጂ ነውና አለበት ድረስ ወስደሀ እሳየኝ፡፡ እናት አባትሀም ቤት ከሆነ ከሩቅ
ልየው:: ዐይኑን አይቼና ኣንድ ጊዜ ስሜው ልሙት!» ብላ ጫፈ ድልዱሙን
ጥቁር ጫማዩን ዕንባ አርከፈከፈችበት። የምይዘውና የምለቀው ጠፋኝ፡፡ ቁርጡን
ለማወቅ ቆርጣ መነሣቷን ስላወቅሁ ኣበይ ተነሽ ልብስሽን ቀያይሪና እንሂድ!
እይተሽው ለመመለስ እንጂ ይዘነው መምጣት አንችልም» አልኳት። እግሬን
ሳትለቅ አሻቅባ እያየች «እኔም ይዤው ልምጣ አልልም፣ ዐይኑን ብቻ አንድ ጊዜ
ልየው፣ በሕይወት መኖሩን ብቻ ልይ!» ብላ የልቧን አውጥታ ተናገረች።
በጉንጫ ላይ የሚንኳለለው ትኩስ እንባ የልቤን የፍቅር ወለል ቦረቦረው።ተነሥታ ወደ ጓዳ ስትገባ አረማመዷ እንኳ አሳዘነኝ። የባዕድ ሀላፊ አግዳሚ ያህል
እንኳ የማይተዋወቀችን እናትና ልጅ እንዴት አድርጌ እንደማስተዋውቅ ጭንቅ
ጥብብ አለኝ፡፡ እማምዬ እያለ በእናቱ ክንዶች ላይ ያልተዘናከተን' አልቅሶ
ያልተባበለን ሕፃን፣ ዐይኑ አይቶ ሕሊናው ያልመዘገባትን፣ አልቅሶም ይሁን በማቅ
ተንከትክቶ ዕቅፏ ላይ ያልተዘረገፈን ልጅ እንዴት አድርጌ እማማዬ እማማ
ለማሰኘት እንደምችል አጀማመሩም ሆነ አፈጻጸሙ ስማይን መቆንጠር መስሎ
በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ልብሷን ቀይራ ብቅ አለች፡፡ ኣጭር ዞማ ጸጉሯ በሚያምር ሐምራዊ ሻሽ ሽብ ተደርጓል፡፡ ኣጠገቤ መጥታ ቆም ካለች በኋላ በል አታጓጓኝ ይኸው መጣሁ! እንሂድ! » ብላ አሰፈሰፈች፡፡
የረሳችውን ሕፃን፡ ልጅሽ ይኸ ነው ብዬ ሳሳያት፣ ኣቅፋው በደስታ ስታለቅስ እና የልጁም በሁኔታው መደናገጥ ገና ከሩቁ አሽቆጠቆጠኝ፡፡
«የምንሄድበት ቦታ እኮ በጣም ሩቅ ነው» አልኳት፡፡ ግድ የለህም ስለ መንገዱ ሰማይ ጥግ ይድረስ፣ እንሂድ ብቻ' » ብላ ቆርጣ መነሳቷን ወደ በሩ በመራመድ ገለጸች፡፡ ከአስራ አምስት ደቂቃ ጉዞ በኋላ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ግቢ ደረስን። ለሁለተኛ ጊዜ ከሴት ጋር ያዩኝ የድርጅቱ ዘበኞችና ሌሉች ሠራተኞች እርስ በርሳቸው በመተያየት ተጎሻሽሙብኝ፡፡
ሕፃናቱ ሁሉ ልዩ ልዩ ቅርዕና መልክ ያላቸው መጫወቻዎችና አሻንጉሊቶች ይዘው በምድረ ግቢው ሜዳ ላይ እንደ እውድማ ዳር ጥሬ ፈስሰዋል፡፡ ኳስ እያንከባለለ የሚጫወተውን፣ ጅዋጅዌ የሚገፈትረውን፣ ወለሉ ላይ
በተሽከርካሪዎቿ እየተገፋች የምትሽከረከር መኪና ይዞ ራን ራን ጵጵ! ቢብ! የሚለውን፣ ሜዳ መኻል እየተሯሯጡ ድብብቆሽ የሚጫወቱትን ሁሉ አየናቸው::
ለጊዜው ልጃችንን ስላጣሁት ዐመዴ ቡን አለ፡፡ እጄን ኮት ኪሴ ውስጥ
ወሽቄ ከቤት እንደ ወጣን የገዛሁለትን ከረሜላ ማሻሸት ጀመርኩ፡፡ የየወዲያነሽ
ዐይኖች በተስፋ ብርሃን ተከበቡ። የናፍቆት ጎተራቸው አፉን ከፈተ። የጉጉቷ ጥም ተንሰፈሰፈ። ዐይኖቿን ቅርብና ሩቅ ድረስ እየላከች ኣየች፡፡ ሰውነቷ የሚንቀጠቀጥ መሰለ። ውሪ ብጤ ሩጭሩጭ እያለ ባጠገቧ ባለፈ ቁጥር ዐይኖቿ እግሮቹን ተከትለው ይጓዙና በዚያው ፈዝዘው ይቀራሉ፡፡
በመኻሉ አንድ አጠር ጠበብ ያለች ነጭ ሱሪ የታጠቀና ዐመድማ ሹራብ
የደረበ ድምቡል ያለ የሚያምር ልጅ ዝንጉርጉር ቢራቢሮ በግራ እጁ ይዞ
እያንደፋደፈና እፍ እያለባት ከፊት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
....የውስጤን ሥቃይና የሕሊናዬን ሰፊ ጠባሳ ጠልቀው ያላዩ የቅርብ
ዘመዶቻችን «ዛሬማ ተበላሽቶ፣ የሱ ነገር እንዲህ ሆኖ ቀረ፡፡ ያየህይራድን የመሰለ
አንበሳ አባት እያለው ወግ ማዕረግ ያለማየቱ...» እያሉ ያጉመተምታሉ፡፡ ከቤት
ውጪ ማደሬ ያለ ማቋረጥ በመዘውተሩ ሁኔታውን መላው ቤተሰብ ከዳር እስከ
ዳር ዐወቀ፡፡ ደግማ ደጋግማ እናቴ እያፈረች፣ እኅቴ በተለይም የእናቴ
ምስጢረኛና የቅርብ ጓደኛ ወይዘሮ አማረች መኝታ ቤት ድረስ እየገቡ፣ ተው
ደግም አይደል የትልቅ ሰውና የጨዋ ልጅ እንዲህ አይደለም፡፡ እናትህ ብታለቅስ
ታደርስብሃለች» እያሉ ለወጉ ያህል ገሠጹኝ፡፡
እኔን የምመክራትና የምዳኛት ወደ ፊትም ሆነ ወደ ኋላ የማስኪዳት እኔው ራሴ ብቻ በመሆኔ የእነርሱን ምክር ሁሉ እንደሚያልፍ የበረዶ ውሽንፍር
ቆጠርኩት። በጠቅላላ መጻሕፍቶቼንና ልብሶቼን ውስጥ ውስጡን አንድ በአንድ
እግዥ ጨረስኩ፡፡ ከሁለትና ከሦስት ቀን አዳር በኋላ ወደ ወላጆቼ ቤት ስገባ ዘና
ብሎ የሚያናግረኝ ሰው አልነበረም፡፡
አባቴም ከቤት ውጪ በተደጋጋሚ ማደሬንና እንደ እናቴም አባባል «መዛተሌን» ቀስ በቀስ ሰማ።
«አግባ! ትዳር ንብረት ያዝ፣ እንደ ማንም የባለጌ ልጅ ሰፈር ለሰፈር
እትልከስከስ፣ ጎጆ ያስከብራል፣ ትዳር ግርማ ሞገስ ነው ያልኩህ ለዚህ ብዬ ነበር፡፡ያለበለዚያ ግን አካለ መጠን ከደረሰ ጐረምሳ ጋር ምን ያታግለኛል» ብሎ
ከነከተቴው ችላ አለኝ፡፡
ዋል አደር ብሎም «አደጋ ብቻ እንዳያገኘው እንጂ ልቡ መለስ
ሲልለትና ያበጠው ልቡ ሲሟሽሽ እንዳረጀች ውሻ ክትት ይላል» አለና ይብሱኑ ስለ እኔ የነበረውን 'አለና የለም ወይ?” እርግፍ አድርጎ ተወ፡፡
የሐሳቤ ተፃራሪ የሆነው አባቴ እንደ አህያ ሬሳ ቢጠላኝም ቅር አላለኝ፡፡ እኔ ግን «ይህ ነው ለሰው ልጅ የሚሰጠው ታላቅ የመኖር ጸጋ ብዬ ከጥላቻው ውስጥ ብርታትና እፎይታ የተሸለምኩ መሰለኝ።
ወደ ወላጆቼ ቤት ባሰኘን ጊዜ ገብቼ ባስፈለገኝ ሰዓት ውልቅ ማለት
ለመድኩ፡፡ እንደ ምኞቴ ሳልዘጋጅና ሳላስበው፣ የኑሮዬንም አዝማሚያ በሚገባ ሳላቅድ ድንገት ባለትዳር በመሆኔ ኑሮ በመጠኑ ተደናገረኝ። ሆኖም ትዳራችን የተመሠረተው በጽኑ ፍቅር ላይ በመሆኑ ፍላጎቴና ጉጉቴ ሁሉ ነጋ ጠባ
ለመሻሻልና አስደሳች ለውጥ ለማግኘት ሆነ። ወትሮ በቀላሉ ደንግጦ ይበረግግ
የነበረው አእምሮዬ የድፍረትና የወኔ ካፈያ ተርከፈከፈበት።
የየወዲያነሽን ቀኝ እጅ ያዝ አደርግና «ዛሬ ምን ያስፈልገናል?» ስላት ዐይን ዐይኔን እያየች እና የኮቴን አዝራሮች በጣቶቿ እየጠራረገች «ካለህማ....ያህል ይበቃኛል» ብላ ገንዘብ ስትጠይቀኝ የትዳርን አያያዝና አመራር ቀስ በቀስ
ለመድነው። በየወዲያነሽ በኩል የተቸገርኩበት ጉዳይ ቢኖር፡ ስትተኛም ይሁን ስትነሣ ስትበላም ይሁን ስትጠጣ አረ ተው ጌታነህ፡ ኧረ ተው! እረ ተው
ልጄን አሳየኝ? ሞቶም እንደሆነ ቁርጡን ንገረኝ ባይኖር ነው እንጂ ቢኖርግ
መቼ እንዲህ ዝም ትለኝ ነበር?» እያለች ስለምትጨቀጭቀኝ ነበር፡፡ ምንም እንኳ
አንዳንድ ነገርን አገላብጠው የማያዩ ቀባጣሪዎች «ጨካኝ አረመኔ ነች» እያሉ
እንደሚያሟትና ወደ ፊትም እንደሚያባጥሏት እያሰብኩ ለጊዜው ብበሳጭም እኔ ከማንም ይበልጥ የእኔዋን እና ቅኗን የወዲያነሽን አሳምሬ ስለማውቃት አባባላቸው ሁሉ ከወሬ እንኳ የነፈሰበት ተራ ወሬ ነው ብዬ እንደ ቤት ጉድፍ ጠራርጌ ጣልኩት።
ያን በማሕፀኗ ዘጠኝ ወር ሙሉ ተሽክማ በስንት የኑሮ ሥቃይ እና ውጣ ውረድ የወለደችውን ልጅዋንና አካሏን ለማየት እያለቀሰች ብታስቸግረኝም
የእናትነት ወጓ በመሆኑ ምንም ቅር አላለኝም፡፡
አንድ ቀን እሑድ ጥዋት ለቁርስ እንደ ተቀመጥን ሳላስበውና
የሚያጋጥመኝን ሳልጠራጠር ከኪሴ እንድ ትንሽ ሰማያዊ ማኅደር አወጣሁ፡፡
በውስጡ የነበሩትን ልዩ ልዩ ሥዕሎች ተራ በተራ ስመለከት የወዲያነሽም
እጅዋን ትከሻዬ ላይ ጣል አድርጋ ትመለከት ነበር፡፡ የልጃችንን ሥዕል ኣየት
እንዳደረገች «ይኸውና» ብላ ባስደንጋጭ ሁኔታ ጮኸች፡፡ ከእጄ ላይ መንጭቃ
ደረቷ ላይ ለጠፈችው።
እነዚያ በእንባ ተኮትኩተው ያደጉት ዐይኖቿ የእንባ ኩልልታ እንጠፈጠፉ፡፡ ሥዕሉን ጠረጴዛው ላይ ወርውራ እግሬ ላይ ዘፍ አለች፡፡ እግሬን ባላት ጠቅላላ ኃይል ቁልቁል ጨምድዳ ስለ ያዘችው ጎትቼ ማላቀቅ አቃተኝ።
«ብዙ ሥቃይና መከራ ያየሁበት፣ ተንገላትቼ የተንከራተትኩበት የበኸር
ልጂ ነውና አለበት ድረስ ወስደሀ እሳየኝ፡፡ እናት አባትሀም ቤት ከሆነ ከሩቅ
ልየው:: ዐይኑን አይቼና ኣንድ ጊዜ ስሜው ልሙት!» ብላ ጫፈ ድልዱሙን
ጥቁር ጫማዩን ዕንባ አርከፈከፈችበት። የምይዘውና የምለቀው ጠፋኝ፡፡ ቁርጡን
ለማወቅ ቆርጣ መነሣቷን ስላወቅሁ ኣበይ ተነሽ ልብስሽን ቀያይሪና እንሂድ!
እይተሽው ለመመለስ እንጂ ይዘነው መምጣት አንችልም» አልኳት። እግሬን
ሳትለቅ አሻቅባ እያየች «እኔም ይዤው ልምጣ አልልም፣ ዐይኑን ብቻ አንድ ጊዜ
ልየው፣ በሕይወት መኖሩን ብቻ ልይ!» ብላ የልቧን አውጥታ ተናገረች።
በጉንጫ ላይ የሚንኳለለው ትኩስ እንባ የልቤን የፍቅር ወለል ቦረቦረው።ተነሥታ ወደ ጓዳ ስትገባ አረማመዷ እንኳ አሳዘነኝ። የባዕድ ሀላፊ አግዳሚ ያህል
እንኳ የማይተዋወቀችን እናትና ልጅ እንዴት አድርጌ እንደማስተዋውቅ ጭንቅ
ጥብብ አለኝ፡፡ እማምዬ እያለ በእናቱ ክንዶች ላይ ያልተዘናከተን' አልቅሶ
ያልተባበለን ሕፃን፣ ዐይኑ አይቶ ሕሊናው ያልመዘገባትን፣ አልቅሶም ይሁን በማቅ
ተንከትክቶ ዕቅፏ ላይ ያልተዘረገፈን ልጅ እንዴት አድርጌ እማማዬ እማማ
ለማሰኘት እንደምችል አጀማመሩም ሆነ አፈጻጸሙ ስማይን መቆንጠር መስሎ
በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ልብሷን ቀይራ ብቅ አለች፡፡ ኣጭር ዞማ ጸጉሯ በሚያምር ሐምራዊ ሻሽ ሽብ ተደርጓል፡፡ ኣጠገቤ መጥታ ቆም ካለች በኋላ በል አታጓጓኝ ይኸው መጣሁ! እንሂድ! » ብላ አሰፈሰፈች፡፡
የረሳችውን ሕፃን፡ ልጅሽ ይኸ ነው ብዬ ሳሳያት፣ ኣቅፋው በደስታ ስታለቅስ እና የልጁም በሁኔታው መደናገጥ ገና ከሩቁ አሽቆጠቆጠኝ፡፡
«የምንሄድበት ቦታ እኮ በጣም ሩቅ ነው» አልኳት፡፡ ግድ የለህም ስለ መንገዱ ሰማይ ጥግ ይድረስ፣ እንሂድ ብቻ' » ብላ ቆርጣ መነሳቷን ወደ በሩ በመራመድ ገለጸች፡፡ ከአስራ አምስት ደቂቃ ጉዞ በኋላ በታክሲ ዕጓለ ማውታ ግቢ ደረስን። ለሁለተኛ ጊዜ ከሴት ጋር ያዩኝ የድርጅቱ ዘበኞችና ሌሉች ሠራተኞች እርስ በርሳቸው በመተያየት ተጎሻሽሙብኝ፡፡
ሕፃናቱ ሁሉ ልዩ ልዩ ቅርዕና መልክ ያላቸው መጫወቻዎችና አሻንጉሊቶች ይዘው በምድረ ግቢው ሜዳ ላይ እንደ እውድማ ዳር ጥሬ ፈስሰዋል፡፡ ኳስ እያንከባለለ የሚጫወተውን፣ ጅዋጅዌ የሚገፈትረውን፣ ወለሉ ላይ
በተሽከርካሪዎቿ እየተገፋች የምትሽከረከር መኪና ይዞ ራን ራን ጵጵ! ቢብ! የሚለውን፣ ሜዳ መኻል እየተሯሯጡ ድብብቆሽ የሚጫወቱትን ሁሉ አየናቸው::
ለጊዜው ልጃችንን ስላጣሁት ዐመዴ ቡን አለ፡፡ እጄን ኮት ኪሴ ውስጥ
ወሽቄ ከቤት እንደ ወጣን የገዛሁለትን ከረሜላ ማሻሸት ጀመርኩ፡፡ የየወዲያነሽ
ዐይኖች በተስፋ ብርሃን ተከበቡ። የናፍቆት ጎተራቸው አፉን ከፈተ። የጉጉቷ ጥም ተንሰፈሰፈ። ዐይኖቿን ቅርብና ሩቅ ድረስ እየላከች ኣየች፡፡ ሰውነቷ የሚንቀጠቀጥ መሰለ። ውሪ ብጤ ሩጭሩጭ እያለ ባጠገቧ ባለፈ ቁጥር ዐይኖቿ እግሮቹን ተከትለው ይጓዙና በዚያው ፈዝዘው ይቀራሉ፡፡
በመኻሉ አንድ አጠር ጠበብ ያለች ነጭ ሱሪ የታጠቀና ዐመድማ ሹራብ
የደረበ ድምቡል ያለ የሚያምር ልጅ ዝንጉርጉር ቢራቢሮ በግራ እጁ ይዞ
እያንደፋደፈና እፍ እያለባት ከፊት
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሥራ ከጀመረ አንድ ዓመት ሞላው። ከእናትና ከእህቱ ተለይቶ በናፍቆታቸው እየተሰቃየ አንድ ድፍን ዓመት አስቆጠረ። በአማረችና በሱ መካከል የተጀመረው ጓደኝነትም ውስጥ ውስጡን የሚያብከነክን የሚያብስለስል ነገር ግን ገሀድ ያልወጣ ድብቅ ቢሆንባቸውም የሙቀት መጠኑንና የእድገት ደረጃውን ጠብቆ በመጓዝ የአንድ ዓመት ልደቱን አከበረ።
ለአዲሱ አለቃው ለልዑል ሰገድ አስጨናቂና ፈታኝ ሰው እየሆነበት
ከመጣ አንድ ዓመት ሞላው። በዩኒቨርስቲ የሚከታተለው ትምህርት አካውንቲንግ መሆኑ በፍጥነት ወደ ሂሳብ ክፍል ለመዛወር ያስቻለው ቢሆንም አዲሱ አለቃው ልኡልሰገድ በዝውውሩ ደስተኛ አልሆነም። ገናለገና በትምህርት ይበልጠኛል የወደፊት የዕድገት ተስፋዬን ያጨልምብኛል በሚል ፍርሃት ጥምድ አድርጎ ይዞታል። በአንፃሩ ደግሞ ከቀድሞው አለቃው ከሽመልስ ጋር የነበራቸው ግንኙነት ተጠናክሮ ላለፈው
አንድ ሙሉ አመት የሚያስቀኑ ጓደኛሞች በመሆን ዘልቀዋል፡፡ ሁለተኛው ዓመትስ በምን ይቀጥል ይሆን? በሱ በኩል ሁለተኛው ዓመት የእናቱንና የተወለደባት ቀዬውን ናፍቆት ለመወጣት የዓመት እረፍት ፈቃዱን ወስዶ ወደ ባሌ የሚሄድበት፣ ከአማረች ጋር ያለው ግንኙነት ይበልጥ የሚጠናከርበት፡ዘይኑን አምጥቶ አዲስ አበባ ትምህርት እንድትጀምር የሚያደርግበት ዓመት እንደሚሆን ዕቅድ ይዟል::
የጌትነት እናት ኑሮዋ እያማረ ደስታዋ እየጨመረ በመሄዱ “ ተመስገን
ፈጣሪዬ ላንተ ምን ይሳንሀል?"እያለች ፈጣሪዋን ማመስገን ከጀመረች አንድ ዓመት ሞላት። ዛሬ ዕድሜ ለጌትነት ችግር ተወግዷል። በየማሳው ላይ እየዋሉ በፀሃይ መጠበስ ቀርቷል። ደብዳቤው በየጊዜው ይጎርፋል አለሁልሽ የሚላት ልጅዋ ያለማቋረጥ ተቆራጭ አድርጎላታል።"ገበያ እንዳትወጪ አቅም የለሽም እኔ አለሁ አይዞሽ!” ነው የሚላት። ወደ ዓመቱ መጨረሻ ላይ የላከው ደብዳቤ ደግሞ በሚቀጥለው ዓመት ዘይኑን ወስዶ ለማስተማር ያለውን ሀሳብ የሚገልጽ ሆነ፡፡ ከእናቷ መለየቷን ባይወደውም በቅርበት አስፈላጊውን ክትትልና እገዛ እያደረገላት ጥሩ ደረጃ ላይ
እንድትደርስ ሌላ አማራጭ አልነበረውምና ይህንኑ ገልፆ ደብዳቤ ለእናቱ ጻፈላት፡፡
እናቱ አስካለ ደብዳቤው ሲደርሳት አላንገራገረችም፡፡ ሀሳቡን በደስታ ተቀበለችው። ዘይኑ ግን ሀሳብዋ ለሁለት ተከፈለ። የወንድሟን ናፍቆት ለመወጣት መሄዱን ስትፈልገው ከእናቷ መለየቱ ደግሞ ሆዷን አባባውና መንታ መንገድ ላይ ቆመች። ትንሿ ዘይኑ ለአንድና ብቸኛ ወንድሟም ሆነ ምትክ ለሌላት እናቷ ያላት ፍቅር እኩል ነው፡፡ እናት ደግሞ ዘይኑን ማጣቷ ትልቅ ጉዳት ነው። በተለይ "ማታ ማታ እቅፍ እያደረገቻት እስቲ ጀርባዬን እከኪልኝ ከፍ ዝቅ ጎሽ! አዎን እንደሱ!" የምትላት ደክሟት ስትገባ ቤቱን አሟሙቃ የምትጠብቃት ጉድ ጉድ የምትልላት
ሁሉ ሊቀር ነው። ዘይኑም ከዚያ ከምትወደው ከሚሞቃት የእናቷ ጉያ
ልትነጠል ነው፡፡ እንኮኮ እያለ ንፍጧን እየጠረገ ያሳደጋት ታላቅ ወንድሟ
ደግሞ የአባቷ ምትክ አባቷም ወንድሟም ነው። ወሬውን ከስማች በኋላ ልቧ ወደ ወንድሟ ሲጋልብ የእናቷ ፍቅር ደግሞ ሉጋም እየሆነባት በሀሳብ ስትባክን ከረመች፡ የስፈሯ ልጆች አዲስ አበባ ወንድም” አላት እያሉ ሲያደንቁላት ሲያጋንኑላት ትሰማለች፡፡ አዲስ አበባ የሚያምር የሚያጓጓ አገር መሆኑን ስለምትስማ የዘይኑ ትንሽ ልብ በመጨረሻ ላይ አዲስ አበባ በመሄድ ሃሳብ ተማረከች፡፡
"ለመሆኑ ልትልኪያት ወሰንሽ?" አሉ ወይዘሮ ዘለቃ የደብዳቤውን
መንፈስ ከተረዱ በኋላ፡፡
"ምን ይደረግ ታዲያ እትዬ ዘለቃ? ትምህርቷን መቀጠል አለባት። ያለበለዚያ ማቋረጧ ነውኮ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ብቸኝነት ነፍሱን ሊያወጣው ነው፡፡ ሄዳ ትማር ሌላ ምንም አማራጭ የለም" አለችና ዘይኑን ትኩር ብላ በጉጉትና በፍቅር አስተዋለቻት፡፡ በዘይኑ ውስጥ አልፋ ጌትነትን ቃኘች እንደ አህያ ጡት ያሏት ሁለት ልጆቿን አንዷን በእውን ሌላውን በምናቧ እያስተዋለች ሳትተነፍስ ለረጅም ጊዜ ፀጥ ብላ ቆየች። ዘይኑ ያንኑ መከረኛ ቡና እያፈላች ነበር፡፡
"አንቺ ዘይኑ አንቺስ ምን አሰብሽ?" ብለው ጠየቋት ወይዘሮ ዘለቃ።
"እኔ ምን አውቃለሁ ሂጂ ካለችኝ እሄዳለሁ ቅሪ ካለችኝ እቀራለሁ" አለች ዘይኑ።
"አየሽ ? አየሽ ?ይቺ መናጢ ልቧ ለመሄድ ከጅሏል ማለት ነው፡፡
እናትሽን ለማን ጥለሽ ነው የምትሄጂው አንቺ?! ትምህርት ቀስ ተብሎ ይደረሳል" አሏት፡፡ አሮጊቷ ልጇን መጨቅጨቃቸውን እናት አልወደደችውም፡፡ ሁለቱ ልጆቿ እርስ በርሳቸው እየተደጋገፉ "ወንድም
ጋሻዬ ዘይንዬ" እየተባባሉ እየተረዳዱ በፍቅር አብረው እንዲኖሩላት ነው
ፍላጎቷ። የራሷ ችግር ብቸኝነቷ አልታያትም፡፡ የነሱ ደስታ ነው ደስታዋ
ወንድሟ ትምጣልኝ ብሎ ከጠየቀ ምንም ማንገራገር አያስፈልግም፡፡ መነሳት ብቻ!
"ይተዋት ባክሁ አልሄድም ብትልስ መቼ እሺ እላታለሁ? ሄዳ ትማር፡፡ ዛሬ ከሁሉ የበለጠው ትምህርት ነው፡፡ ጌትዬም ሰው ሆኖ አለሁልሽ የሚለኝ ቢማር አይደል? ዋ! ልጄ በዚህ ላይ ደግሞ ማን አለው? ብቻውን በሰው ሀገር። ትሂድለትና ልቡ ትንሽ አረፍ ይበልንጂ...
የሱ ልብ ሳያርፍ እኔስ የምተኛው እንቅልፍ ምን እንቅልፍ ይሆነኛል? ትርፉ ቅዠት ነው" ዘይኑ በእናቷ አነጋገር ደስ አላት። በልቧ የአሮጊቷን ንግግር አልወደደችውም ነበር። ወደ ወንድም ጋሻዋ በሃሳቧ ተጓዘች።
አዲስ አበባ! ጓደኞቿ የሚያደንቁት ቆንጆ ከተማ! አዲስ አበባ ሄዳ ከወንድሟ ጋር የመኖሩ ነገር በጉጉት ታያት። ልቧ ወደ መሄዱ አደላ። አቤት የዘይኑ ነገር! ደስታ በደስታ ሆነች። ደግሞ ተደስታ ብዙ አልቆየችም፡፡
የእናቷ ነገር መጥቶ እንደገና ከፊቷ ድቅን አለባትና አለቀሰች። ማን እማምዬ እያለ ጀርባዋን ያሻሻታል? ማን ቡና ያፈላላታል? ማን ቤቱን ይጠራርግላታል? እናቷ በብዙ ነገር እንደምትጎዳባት ታያት። ኦና ቤት
ጣራና ግድግዳ ብቻ! አቤት ጣራና ግድግዳ ሰው ከሌለበት ሲያስጠላ?!
እንኳን ደሳሳ ጎጆ የተንጣለለ ቪላ ቤትም ቢሆን ያለሰው አያምርም። እሷ
እንደዚህ ትጨነቅ እንጂ እናቷ እንደሆነች ቆርጣለች። እህቴ ትምጣልኝ
ብሎ ከጠየቀ ጊዜ ሳታጠፋ ቶሎ ልትልክለት ወስናለች።
እናትነት ሰው በመሆን አስተዋይነት ውስጥ ብቻ ሳይሆን ሳይዘሩ ሳያርሙና ሳይኮተኩቱ በርረው በሚኖሩ አእዋፋት ላይ እንኳ ሚስጥሩ ረቂቅ ነው፡፡ ለልጇ ስትል ከድመትና ከጨለሌ ጋር ጦርነት ገጥማ በክንፏም በጥፍሯም ታግላ የምትከላከል ዶሮ፣ ግልገሏ ወደ ገደል ስትወረወር ረጅዋን ተከትላ ወደ ገደሉ የወረደችው አህያ እናት ለልጅዋ ያላትን
ልቅ ፍቅር የሚገልፅ ነው። ዘይኑም ይህንን በደንብ ታውቀዋለች። የሶስተኛ ክፍል ተማሪ ሆና ባነበበችው የተረት መፅሐፍ ውስጥ በጫካ የምትኖር ዋኔ ጫጩቶችዋን በጉያዋ እንዳቀፈች ከተነሳው የሰደድ እሳት ልታስጥላቸው የከፈለችውን የህይወት ዋጋ ታውቃለች። እሳቱን ፈርታ ሳትደነብር ሳትበረግግ ጫጩቶችዋን ለማዳን እንዳቀፈቻቸው በነበልባሉ ተጠብሳና ተቃጥላ ስትሞት በስሯ የተጠለሉት ጫጩቶች በሙሉ ሳይቃጠሉ መትረፋቸውን አንብባ የእናት ፍቅር ምን ያክል ከባድ እንደሆነ አስ
ደንቋታል። የዚያን ያክል ጥሩ እናቶች እንዳሉ ሁሉ ለልጆቻቸው ደንታ ቢስ የሆኑ ምንም አይነት የልጅ ፍቅር የሌላቸው የወለዱትን እያስራቡ ሆቴል ገብተው ጮማ የሚቆርጡ ወላጆች መኖራቸው የሚካድ ኣይደለም፡፡ አንዳንዴ የእናት አንጀት ከጨከነ ከደነደነ ቦታውን የሚረከበው ክፉ መንፈስ ይሆንና የወለዱትን ልጅ ጫካ ውስጥ እንደ ውሻ ወርውሮ እስከ መጥፋትና በምናምን ጠቅልሎ ሽንት ቤት ውስጥ እስከ መጨመር ያደርሳል
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ሥራ ከጀመረ አንድ ዓመት ሞላው። ከእናትና ከእህቱ ተለይቶ በናፍቆታቸው እየተሰቃየ አንድ ድፍን ዓመት አስቆጠረ። በአማረችና በሱ መካከል የተጀመረው ጓደኝነትም ውስጥ ውስጡን የሚያብከነክን የሚያብስለስል ነገር ግን ገሀድ ያልወጣ ድብቅ ቢሆንባቸውም የሙቀት መጠኑንና የእድገት ደረጃውን ጠብቆ በመጓዝ የአንድ ዓመት ልደቱን አከበረ።
ለአዲሱ አለቃው ለልዑል ሰገድ አስጨናቂና ፈታኝ ሰው እየሆነበት
ከመጣ አንድ ዓመት ሞላው። በዩኒቨርስቲ የሚከታተለው ትምህርት አካውንቲንግ መሆኑ በፍጥነት ወደ ሂሳብ ክፍል ለመዛወር ያስቻለው ቢሆንም አዲሱ አለቃው ልኡልሰገድ በዝውውሩ ደስተኛ አልሆነም። ገናለገና በትምህርት ይበልጠኛል የወደፊት የዕድገት ተስፋዬን ያጨልምብኛል በሚል ፍርሃት ጥምድ አድርጎ ይዞታል። በአንፃሩ ደግሞ ከቀድሞው አለቃው ከሽመልስ ጋር የነበራቸው ግንኙነት ተጠናክሮ ላለፈው
አንድ ሙሉ አመት የሚያስቀኑ ጓደኛሞች በመሆን ዘልቀዋል፡፡ ሁለተኛው ዓመትስ በምን ይቀጥል ይሆን? በሱ በኩል ሁለተኛው ዓመት የእናቱንና የተወለደባት ቀዬውን ናፍቆት ለመወጣት የዓመት እረፍት ፈቃዱን ወስዶ ወደ ባሌ የሚሄድበት፣ ከአማረች ጋር ያለው ግንኙነት ይበልጥ የሚጠናከርበት፡ዘይኑን አምጥቶ አዲስ አበባ ትምህርት እንድትጀምር የሚያደርግበት ዓመት እንደሚሆን ዕቅድ ይዟል::
የጌትነት እናት ኑሮዋ እያማረ ደስታዋ እየጨመረ በመሄዱ “ ተመስገን
ፈጣሪዬ ላንተ ምን ይሳንሀል?"እያለች ፈጣሪዋን ማመስገን ከጀመረች አንድ ዓመት ሞላት። ዛሬ ዕድሜ ለጌትነት ችግር ተወግዷል። በየማሳው ላይ እየዋሉ በፀሃይ መጠበስ ቀርቷል። ደብዳቤው በየጊዜው ይጎርፋል አለሁልሽ የሚላት ልጅዋ ያለማቋረጥ ተቆራጭ አድርጎላታል።"ገበያ እንዳትወጪ አቅም የለሽም እኔ አለሁ አይዞሽ!” ነው የሚላት። ወደ ዓመቱ መጨረሻ ላይ የላከው ደብዳቤ ደግሞ በሚቀጥለው ዓመት ዘይኑን ወስዶ ለማስተማር ያለውን ሀሳብ የሚገልጽ ሆነ፡፡ ከእናቷ መለየቷን ባይወደውም በቅርበት አስፈላጊውን ክትትልና እገዛ እያደረገላት ጥሩ ደረጃ ላይ
እንድትደርስ ሌላ አማራጭ አልነበረውምና ይህንኑ ገልፆ ደብዳቤ ለእናቱ ጻፈላት፡፡
እናቱ አስካለ ደብዳቤው ሲደርሳት አላንገራገረችም፡፡ ሀሳቡን በደስታ ተቀበለችው። ዘይኑ ግን ሀሳብዋ ለሁለት ተከፈለ። የወንድሟን ናፍቆት ለመወጣት መሄዱን ስትፈልገው ከእናቷ መለየቱ ደግሞ ሆዷን አባባውና መንታ መንገድ ላይ ቆመች። ትንሿ ዘይኑ ለአንድና ብቸኛ ወንድሟም ሆነ ምትክ ለሌላት እናቷ ያላት ፍቅር እኩል ነው፡፡ እናት ደግሞ ዘይኑን ማጣቷ ትልቅ ጉዳት ነው። በተለይ "ማታ ማታ እቅፍ እያደረገቻት እስቲ ጀርባዬን እከኪልኝ ከፍ ዝቅ ጎሽ! አዎን እንደሱ!" የምትላት ደክሟት ስትገባ ቤቱን አሟሙቃ የምትጠብቃት ጉድ ጉድ የምትልላት
ሁሉ ሊቀር ነው። ዘይኑም ከዚያ ከምትወደው ከሚሞቃት የእናቷ ጉያ
ልትነጠል ነው፡፡ እንኮኮ እያለ ንፍጧን እየጠረገ ያሳደጋት ታላቅ ወንድሟ
ደግሞ የአባቷ ምትክ አባቷም ወንድሟም ነው። ወሬውን ከስማች በኋላ ልቧ ወደ ወንድሟ ሲጋልብ የእናቷ ፍቅር ደግሞ ሉጋም እየሆነባት በሀሳብ ስትባክን ከረመች፡ የስፈሯ ልጆች አዲስ አበባ ወንድም” አላት እያሉ ሲያደንቁላት ሲያጋንኑላት ትሰማለች፡፡ አዲስ አበባ የሚያምር የሚያጓጓ አገር መሆኑን ስለምትስማ የዘይኑ ትንሽ ልብ በመጨረሻ ላይ አዲስ አበባ በመሄድ ሃሳብ ተማረከች፡፡
"ለመሆኑ ልትልኪያት ወሰንሽ?" አሉ ወይዘሮ ዘለቃ የደብዳቤውን
መንፈስ ከተረዱ በኋላ፡፡
"ምን ይደረግ ታዲያ እትዬ ዘለቃ? ትምህርቷን መቀጠል አለባት። ያለበለዚያ ማቋረጧ ነውኮ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ብቸኝነት ነፍሱን ሊያወጣው ነው፡፡ ሄዳ ትማር ሌላ ምንም አማራጭ የለም" አለችና ዘይኑን ትኩር ብላ በጉጉትና በፍቅር አስተዋለቻት፡፡ በዘይኑ ውስጥ አልፋ ጌትነትን ቃኘች እንደ አህያ ጡት ያሏት ሁለት ልጆቿን አንዷን በእውን ሌላውን በምናቧ እያስተዋለች ሳትተነፍስ ለረጅም ጊዜ ፀጥ ብላ ቆየች። ዘይኑ ያንኑ መከረኛ ቡና እያፈላች ነበር፡፡
"አንቺ ዘይኑ አንቺስ ምን አሰብሽ?" ብለው ጠየቋት ወይዘሮ ዘለቃ።
"እኔ ምን አውቃለሁ ሂጂ ካለችኝ እሄዳለሁ ቅሪ ካለችኝ እቀራለሁ" አለች ዘይኑ።
"አየሽ ? አየሽ ?ይቺ መናጢ ልቧ ለመሄድ ከጅሏል ማለት ነው፡፡
እናትሽን ለማን ጥለሽ ነው የምትሄጂው አንቺ?! ትምህርት ቀስ ተብሎ ይደረሳል" አሏት፡፡ አሮጊቷ ልጇን መጨቅጨቃቸውን እናት አልወደደችውም፡፡ ሁለቱ ልጆቿ እርስ በርሳቸው እየተደጋገፉ "ወንድም
ጋሻዬ ዘይንዬ" እየተባባሉ እየተረዳዱ በፍቅር አብረው እንዲኖሩላት ነው
ፍላጎቷ። የራሷ ችግር ብቸኝነቷ አልታያትም፡፡ የነሱ ደስታ ነው ደስታዋ
ወንድሟ ትምጣልኝ ብሎ ከጠየቀ ምንም ማንገራገር አያስፈልግም፡፡ መነሳት ብቻ!
"ይተዋት ባክሁ አልሄድም ብትልስ መቼ እሺ እላታለሁ? ሄዳ ትማር፡፡ ዛሬ ከሁሉ የበለጠው ትምህርት ነው፡፡ ጌትዬም ሰው ሆኖ አለሁልሽ የሚለኝ ቢማር አይደል? ዋ! ልጄ በዚህ ላይ ደግሞ ማን አለው? ብቻውን በሰው ሀገር። ትሂድለትና ልቡ ትንሽ አረፍ ይበልንጂ...
የሱ ልብ ሳያርፍ እኔስ የምተኛው እንቅልፍ ምን እንቅልፍ ይሆነኛል? ትርፉ ቅዠት ነው" ዘይኑ በእናቷ አነጋገር ደስ አላት። በልቧ የአሮጊቷን ንግግር አልወደደችውም ነበር። ወደ ወንድም ጋሻዋ በሃሳቧ ተጓዘች።
አዲስ አበባ! ጓደኞቿ የሚያደንቁት ቆንጆ ከተማ! አዲስ አበባ ሄዳ ከወንድሟ ጋር የመኖሩ ነገር በጉጉት ታያት። ልቧ ወደ መሄዱ አደላ። አቤት የዘይኑ ነገር! ደስታ በደስታ ሆነች። ደግሞ ተደስታ ብዙ አልቆየችም፡፡
የእናቷ ነገር መጥቶ እንደገና ከፊቷ ድቅን አለባትና አለቀሰች። ማን እማምዬ እያለ ጀርባዋን ያሻሻታል? ማን ቡና ያፈላላታል? ማን ቤቱን ይጠራርግላታል? እናቷ በብዙ ነገር እንደምትጎዳባት ታያት። ኦና ቤት
ጣራና ግድግዳ ብቻ! አቤት ጣራና ግድግዳ ሰው ከሌለበት ሲያስጠላ?!
እንኳን ደሳሳ ጎጆ የተንጣለለ ቪላ ቤትም ቢሆን ያለሰው አያምርም። እሷ
እንደዚህ ትጨነቅ እንጂ እናቷ እንደሆነች ቆርጣለች። እህቴ ትምጣልኝ
ብሎ ከጠየቀ ጊዜ ሳታጠፋ ቶሎ ልትልክለት ወስናለች።
እናትነት ሰው በመሆን አስተዋይነት ውስጥ ብቻ ሳይሆን ሳይዘሩ ሳያርሙና ሳይኮተኩቱ በርረው በሚኖሩ አእዋፋት ላይ እንኳ ሚስጥሩ ረቂቅ ነው፡፡ ለልጇ ስትል ከድመትና ከጨለሌ ጋር ጦርነት ገጥማ በክንፏም በጥፍሯም ታግላ የምትከላከል ዶሮ፣ ግልገሏ ወደ ገደል ስትወረወር ረጅዋን ተከትላ ወደ ገደሉ የወረደችው አህያ እናት ለልጅዋ ያላትን
ልቅ ፍቅር የሚገልፅ ነው። ዘይኑም ይህንን በደንብ ታውቀዋለች። የሶስተኛ ክፍል ተማሪ ሆና ባነበበችው የተረት መፅሐፍ ውስጥ በጫካ የምትኖር ዋኔ ጫጩቶችዋን በጉያዋ እንዳቀፈች ከተነሳው የሰደድ እሳት ልታስጥላቸው የከፈለችውን የህይወት ዋጋ ታውቃለች። እሳቱን ፈርታ ሳትደነብር ሳትበረግግ ጫጩቶችዋን ለማዳን እንዳቀፈቻቸው በነበልባሉ ተጠብሳና ተቃጥላ ስትሞት በስሯ የተጠለሉት ጫጩቶች በሙሉ ሳይቃጠሉ መትረፋቸውን አንብባ የእናት ፍቅር ምን ያክል ከባድ እንደሆነ አስ
ደንቋታል። የዚያን ያክል ጥሩ እናቶች እንዳሉ ሁሉ ለልጆቻቸው ደንታ ቢስ የሆኑ ምንም አይነት የልጅ ፍቅር የሌላቸው የወለዱትን እያስራቡ ሆቴል ገብተው ጮማ የሚቆርጡ ወላጆች መኖራቸው የሚካድ ኣይደለም፡፡ አንዳንዴ የእናት አንጀት ከጨከነ ከደነደነ ቦታውን የሚረከበው ክፉ መንፈስ ይሆንና የወለዱትን ልጅ ጫካ ውስጥ እንደ ውሻ ወርውሮ እስከ መጥፋትና በምናምን ጠቅልሎ ሽንት ቤት ውስጥ እስከ መጨመር ያደርሳል
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ሳትታሰብ የተገኘቶው ትርፌ በጋሻው ለብዙዎች ያልታሰበ ደስታ
እስግኝታለች፡፡ ከሁሉም በላይ አስቻለው ተመችቶታል፡፡ ቤቱ ተዘግቶ አይውልም አይዝረከረክም፣ ኦይመሰቃቀልም፤ ትርፌ ሽክፍ አደርጋ ይዛዋለች። የሆቴል ምግብ
ትቶ ቤቱ ውስጥ መመገብ ጀምሯል። እንጻራዊ የሆነ የመንፈስ መረጋጋትም አግኝቷል፡፡ በልሁና መርዕድ እንኳ እንደ ድሮው ፍራሽ በማንጠፍ ከሰል
በማያያዝና ሻይ ወይም ቡና በማፍላት ተራ መጨቃጨቃቸውን ትተዋል።ጫታቸውን ብቻ ገዝተው በተነጠፈና በተበጃጀ ፍራሽ ላይ እግራቸውን መዘርጋት ነው፡፡ ቀሪውን ስራ ትርፌ ታቀለጣጥፈው ይዛለች፡፡
የትርፈ በአስቻለው ቤት ተመልሳ መግባት ለሔዋንም የፀጋ ያህል ሆኗል።ሔዋን የአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰደች በኋላ በወቅቱ ግዳጅ በነበረው የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ሥራ በመጀመሯ በከፊልም ቢሆን ከሸዋዬ ቁጥጥር ውጭ ሆናለች። አጋጣሚ ሆና የተመደበችው ደግሞ በዚያው በዲላ ከተማ
በዜሮ ስምንት ቀበሌ ውስጥ በመሆን ከቤት ወደ ስራ ከስራ ወደ ቤት የምትመላለሰው በአስቻለው ቤት በር ላይ ነው። እናም ስታልፍ ስታንድም ጎራ
ትልበታለች። ትርፌ ስላለች ዘወትር ክፍት ነውና አትቸገርም። ይህ ሁኔታ በእሷና በትርፌ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮት መነፋፈቅ ጀምረዋል።
አንድ ቀን ደግሞ ሁለቱን ለረጅም ሰዓት አብሮ የሚያቆይ አጋጣሚ
ተፈጠረ፡፡ የግንቦት ወር መጨረሻ አካባቢ ነው ሔዋን መሰረተ ትምህርት በምታስተምርበት ጣቢያ አካባቢ አንዲት ሴት ሞተው በለቅሶው ምክንያት በዕለቱ ማስተማር እንደማትችል ከጣቢያ ሃላፊው ይነገራታል፡፡ ከጠዋቱ ሦስት ሠዓት
አካባቢ ወደ ቤቷ ስትመለስ እግረ መንገዷን ወደ አስቻለው ቤት ጎራ ትላለች። ጊዜ ነበራትና ተረጋግታ ቁጭ በማለት ከትርፌ ጋራ ጭውውት ይጀምራሉ። ሔዋን
በአስቻለው አልጋ ላይ ትራስ ደገፍ ብላ ፣ ትርፌ ደግሞ በአልጋው ትይዩ በተነጠፈችው ፍራሽ ላይ ሆና ፊትለፊት እየተያዩ ይጫወታሉ።
«ትርፍዬ!» ስትል ጠራቻት ሔዋን፡
«ወይ እታለም፡፡»
«አገርሽ የት ነው?»
«ውይይ… እታለምዬ! በጣም ሩቅ ነው፣ ቢጠሩት እንኳ አይሰማም፡፡»
ትርፌ የገጠር ኑሮዋ ባያጎሳቁላት ኖሮ ቀይና ስልክክ ያለች፣ ዓይንና
ጥርሶቿ እዩኝ እዩኝ የሚሉ መልከ ቀና የነበረች ልጅ ትመስላለች፡፡ ያም ሆኖ አሁን ወደ አስቻለው ቤት ከተመለሰች ወዲህ ወዘናዋ እየተመለሰ መጥቷል።
«የት ቢሆን ነው ትርፍዬ?» ስትል ሔዋን ደግማ ጠየቀቻት የትርፌን
ሁለመና አየት ሰለል እያደረገች።
«ወሎዬ ነኝ፡፡»
«ውይይ... ከዚያ እዚህ ድረስ አንዴት መጣሽ?»
«ታሪኩ ብዙ ነው እታለም። ደግሞም ያሳዝናል።»
«እንዴት ትርፌ»
«በቃ ያሳዝናል፡፡»
«ከመማጣሽ ግን ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?»
«ወደ አስር ዓመት ሊሆነኝ ነው፡፡»
«ውይይ..» አለችና ሔዋን አሁንም ግን «ግን እንዴት መጣሽ?» ስትል
ጠየቀቻት
«ተጣጥዬ»
“ማለት?»
«የወሎ ድርቅ ሲባል ሰምተሽ ታውቂያለሽ?»
«አዎ»
«በድርቁ ዘመን እኔ ህጣን ልጅ ነብርኩ። የተወለድኩት ውጫሌ እሚባል ቦታ ነው።ያኔ በድርቁ ጊዜ በአገሩ ላይ የሚበላም የሚጠጣም ጠፋ። የአገሩ ሰው ሁሉ ተነቅሎ ተሰደደ።አባቴ በድርቁ ምክንያት ቀደም ብሎ ሞቶ ስለነበር እኔና እናቴም ሕዝቡ ሲሰደድ አብረን ተሰደድን
«ወደዚህ ወደ ሲዳሞ?»
«አይደለም ወደ ደሴ ወደሚባል ከተማ ነው።»
«ታዲያ እዚያ የሚበላና የሚጠጣ አገኛችሁ?»
«እየየ እታለም! ምን ይገኛል ብለሽ? ጣጣው ብዙ ነበር፡፡» አለችና ትርፌ አሁንም በትካዜ ባህር ውስጥ ገባች፡፡ ያን በልጅነት አዕምሮዋ የተቀረፀ የርሀብ
ሁኔታ የቻለችውን ያህል ለማስታወስ ትሞክር ጀመር፡፡ ትርፌ የዚያን ጊዜ ገና
የስድስት ወይም ሰባት ዓመት ህጻን ስለነበረች ሁሉን ነገር አታውቀውም እንጂ ሁኔታው እጅጉን አሳዛኝ ነበር፡፡
«አዎ፡ እንደ ሰው ጨክኗል! የወሎ ሰማያ፡፡ ከዝናብ ሰጪ ደመናዎች ጋር ላይታረቅ የተጣላ ይመስል ቁልጭ ጥርት እንዳላ ድፍን ሶስት ዓመታት አለፉ።ፀሐይና ጨረታ ለእንዴ እንኳ በደመና ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያሉ የአየሁሽ ጨዋታ
ሳይጫወቱ በጠራው ሰማይ ላይ ተንቀለቀሉበት፡፡ በተለይ ፀሐይ በየቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ሙሉ እየነደደች የወሎን ምድር ታነደውና ታቃጥለው ጀመር።ወንዞች ነጠፉ። ሳር ቅጠሉ ደረቀ። ዛፎች ወደ ጭራሮነት ተቀየሩ። ቢመጣ ንፋስ ቢነሳ አቧራ ብቻ ሆነ።
የወሎ ገበሬ የመጀመሪያውን የድርቅ ዓመት ቀድሞ የነበረውን ጥሪት ተጠቅሞ ሳይደናገጥ ተወጥቶት ነበር። የሁለተኛው ግን ወገቡን ሰበረው፡፡ ሶስተኛው ደግሞ ከሥሩ ነቀለው፡፡ እንኳን ለራሱ ለሰንጋ ፈረሱ የእህል ዓይነት ይመርጥ እንዳልነበረ ሁሉ እንኳን ያቀምሰው የሚቀምሰውም አጣ፡፡ በሰንጋ ፈረስ ይጋልብ የነበረ የወሎ መኳንንት፤ በሲናር በቅሎ ስትፈስ የነበረች የወሎ ወይዛዝርት ሁሉ እርካባቸው ወለቀ። ግላሳቸው ተጠቀለለ። በቅሎና ፈረሶቻቸው የአውሬና የአዕዋፍ
ሲሳይ ሆኑ። አጥንቶቻቸው ሜዳ ሙሉ ተረጩ። የረገመው ሳይታወቅ ወሎ ምዕዓት ወረደበት። የረሀብ እሳት ያቃጥለው ጀመር፡፡ በቸነፈር ተመታ።
በዚያን ጊዜ፣ በዚያን ዘመን፣ የወሎ ሕዝብ ምርጫው አንድ ብቻ ነበር፤ ስደት። አቅጣጫው ደግሞ ወደ ደሴ ከተማ፡፡ ይህም ምክንያት ነበረው፡፡ የወቅቱ
ንጉሥ ለጉብኝት ደሴ ከተማ እንደሚገቡ ተወርቶ ነበር፡፡ እሳቸው ደግሞ በሄዱበት ሁሉ ለልጆች ከረሜላ በመርጨታቸው ብቻ የቸርነት ዝናን ያተረፉ ነበሩና
የወሎ ርሃብተኛ ወደ «ቸሩ» ንጉስ በመሄድ የልመና እጁቹን ለመዘርጋት ዳር አስከዳር ተነጋግሮ ወደ ደሴ መጓዝ መትመም ጀመረ።
ከሰሜን አቅጣጫ የራያና የየጁ ሕዝብ በርሀብ የመነመነ ሰውነቱን
ብጥቅጣቂ ጨርቅ እየሸፈነ ሰንሰለት ሰርቶ ወደ ደሴ ሲግተለተል የአንባሰል ተራሮች ቁልቁል እየተመለከቱ ይታዘቡ ነበር፡፡ ከምዕራብና ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ የቦረና! የወረሂመኖ፣ የሳስታና የወገልጤና ሕዝብ ተነቅንቆ ወደ ደሴ ሲጓን በመሀል እየደከመው በገሪዶና በቦሩ ሜዳ ላይ ሲፈስ የጦሳ ተራራ መዓል ላይ ቆሞ ግራና ቀኝ እየተመለከተ ያለቅስ ነበር፡፡ ከምስራቅና ከደቡብ ምሥራቅ
ደግሞ የአውሳ የቃሎ፣ የእንቻሮና የከሚሴ ሕዝብ በበረሃ አለባበስ ዘይቤው ከወገብ በታች ሽርጥ መሳይ አገልድሞ ከወገቡ በላይ ሲያዩት ግጠው ግጠው የጣሉት
አጥንት መስሎ ወደ ደሴ ሲተምም የቦርከና ወንዝ «እናንተስ ወደ ንጉሳችሁ ሄዳችሁ፤ የእኔንስ ችግር ለአባይና ለተከዜ ማን ይንገርልኝ»
እያለ የሚያዝን ይመስል ነበር፡፡
በጋ ከክረምት የውሃ ፈረሰኛ ሲያጓራበት እንዳልነበረ ሁሉ ያኔ ግን ክው ብሎ ደርቋልና በውስጡ የነበሩ ቋጥኛች ጨው መስለው የፀሐይ ንዳድ እየፈነከታቸው ነበር፡፡
ያ ሁሉ የወሎ ርሀብተኛ በዚህ መልክ ተጉዞ ተጉዞ ደሴ ከተማ ሲደርስ ያሰበው አልሆነለትም። እንዲያውም ወደ መሀል ደሴ ከተማ መግባት እንኳ ሳይፈቀድለት ቀረ። የንጉሡ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊሶች በየመጣበት አቅጣጫ ተሰልፈው ጠበቁት። ከስሜን በኩል የመጣውን በሮቢት ገበያ ላይ፣ ከምዕራብ በኩል የመጣውን ከሰኞ ገበያ ላይ እንዲሁም ከምስራቅና ደቡብ ምስራቅ እቅጣጫ የመጣውን
ርሀብተኛ ሀረጎ አፋፍ ላይ በተሰራ የእንጨት አጥር ውስጥ እያስገቡ አጎሩት። በቀን አንዳንድ ዳቦ ለእያንዳንዱ ርሀብተኛ እንደ ውሻ ይጥሉለት ጀመር፡፡ እንዳይነቃነቅ ይጠብቁትም ጀመር።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...ሳትታሰብ የተገኘቶው ትርፌ በጋሻው ለብዙዎች ያልታሰበ ደስታ
እስግኝታለች፡፡ ከሁሉም በላይ አስቻለው ተመችቶታል፡፡ ቤቱ ተዘግቶ አይውልም አይዝረከረክም፣ ኦይመሰቃቀልም፤ ትርፌ ሽክፍ አደርጋ ይዛዋለች። የሆቴል ምግብ
ትቶ ቤቱ ውስጥ መመገብ ጀምሯል። እንጻራዊ የሆነ የመንፈስ መረጋጋትም አግኝቷል፡፡ በልሁና መርዕድ እንኳ እንደ ድሮው ፍራሽ በማንጠፍ ከሰል
በማያያዝና ሻይ ወይም ቡና በማፍላት ተራ መጨቃጨቃቸውን ትተዋል።ጫታቸውን ብቻ ገዝተው በተነጠፈና በተበጃጀ ፍራሽ ላይ እግራቸውን መዘርጋት ነው፡፡ ቀሪውን ስራ ትርፌ ታቀለጣጥፈው ይዛለች፡፡
የትርፈ በአስቻለው ቤት ተመልሳ መግባት ለሔዋንም የፀጋ ያህል ሆኗል።ሔዋን የአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰደች በኋላ በወቅቱ ግዳጅ በነበረው የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ሥራ በመጀመሯ በከፊልም ቢሆን ከሸዋዬ ቁጥጥር ውጭ ሆናለች። አጋጣሚ ሆና የተመደበችው ደግሞ በዚያው በዲላ ከተማ
በዜሮ ስምንት ቀበሌ ውስጥ በመሆን ከቤት ወደ ስራ ከስራ ወደ ቤት የምትመላለሰው በአስቻለው ቤት በር ላይ ነው። እናም ስታልፍ ስታንድም ጎራ
ትልበታለች። ትርፌ ስላለች ዘወትር ክፍት ነውና አትቸገርም። ይህ ሁኔታ በእሷና በትርፌ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮት መነፋፈቅ ጀምረዋል።
አንድ ቀን ደግሞ ሁለቱን ለረጅም ሰዓት አብሮ የሚያቆይ አጋጣሚ
ተፈጠረ፡፡ የግንቦት ወር መጨረሻ አካባቢ ነው ሔዋን መሰረተ ትምህርት በምታስተምርበት ጣቢያ አካባቢ አንዲት ሴት ሞተው በለቅሶው ምክንያት በዕለቱ ማስተማር እንደማትችል ከጣቢያ ሃላፊው ይነገራታል፡፡ ከጠዋቱ ሦስት ሠዓት
አካባቢ ወደ ቤቷ ስትመለስ እግረ መንገዷን ወደ አስቻለው ቤት ጎራ ትላለች። ጊዜ ነበራትና ተረጋግታ ቁጭ በማለት ከትርፌ ጋራ ጭውውት ይጀምራሉ። ሔዋን
በአስቻለው አልጋ ላይ ትራስ ደገፍ ብላ ፣ ትርፌ ደግሞ በአልጋው ትይዩ በተነጠፈችው ፍራሽ ላይ ሆና ፊትለፊት እየተያዩ ይጫወታሉ።
«ትርፍዬ!» ስትል ጠራቻት ሔዋን፡
«ወይ እታለም፡፡»
«አገርሽ የት ነው?»
«ውይይ… እታለምዬ! በጣም ሩቅ ነው፣ ቢጠሩት እንኳ አይሰማም፡፡»
ትርፌ የገጠር ኑሮዋ ባያጎሳቁላት ኖሮ ቀይና ስልክክ ያለች፣ ዓይንና
ጥርሶቿ እዩኝ እዩኝ የሚሉ መልከ ቀና የነበረች ልጅ ትመስላለች፡፡ ያም ሆኖ አሁን ወደ አስቻለው ቤት ከተመለሰች ወዲህ ወዘናዋ እየተመለሰ መጥቷል።
«የት ቢሆን ነው ትርፍዬ?» ስትል ሔዋን ደግማ ጠየቀቻት የትርፌን
ሁለመና አየት ሰለል እያደረገች።
«ወሎዬ ነኝ፡፡»
«ውይይ... ከዚያ እዚህ ድረስ አንዴት መጣሽ?»
«ታሪኩ ብዙ ነው እታለም። ደግሞም ያሳዝናል።»
«እንዴት ትርፌ»
«በቃ ያሳዝናል፡፡»
«ከመማጣሽ ግን ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?»
«ወደ አስር ዓመት ሊሆነኝ ነው፡፡»
«ውይይ..» አለችና ሔዋን አሁንም ግን «ግን እንዴት መጣሽ?» ስትል
ጠየቀቻት
«ተጣጥዬ»
“ማለት?»
«የወሎ ድርቅ ሲባል ሰምተሽ ታውቂያለሽ?»
«አዎ»
«በድርቁ ዘመን እኔ ህጣን ልጅ ነብርኩ። የተወለድኩት ውጫሌ እሚባል ቦታ ነው።ያኔ በድርቁ ጊዜ በአገሩ ላይ የሚበላም የሚጠጣም ጠፋ። የአገሩ ሰው ሁሉ ተነቅሎ ተሰደደ።አባቴ በድርቁ ምክንያት ቀደም ብሎ ሞቶ ስለነበር እኔና እናቴም ሕዝቡ ሲሰደድ አብረን ተሰደድን
«ወደዚህ ወደ ሲዳሞ?»
«አይደለም ወደ ደሴ ወደሚባል ከተማ ነው።»
«ታዲያ እዚያ የሚበላና የሚጠጣ አገኛችሁ?»
«እየየ እታለም! ምን ይገኛል ብለሽ? ጣጣው ብዙ ነበር፡፡» አለችና ትርፌ አሁንም በትካዜ ባህር ውስጥ ገባች፡፡ ያን በልጅነት አዕምሮዋ የተቀረፀ የርሀብ
ሁኔታ የቻለችውን ያህል ለማስታወስ ትሞክር ጀመር፡፡ ትርፌ የዚያን ጊዜ ገና
የስድስት ወይም ሰባት ዓመት ህጻን ስለነበረች ሁሉን ነገር አታውቀውም እንጂ ሁኔታው እጅጉን አሳዛኝ ነበር፡፡
«አዎ፡ እንደ ሰው ጨክኗል! የወሎ ሰማያ፡፡ ከዝናብ ሰጪ ደመናዎች ጋር ላይታረቅ የተጣላ ይመስል ቁልጭ ጥርት እንዳላ ድፍን ሶስት ዓመታት አለፉ።ፀሐይና ጨረታ ለእንዴ እንኳ በደመና ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያሉ የአየሁሽ ጨዋታ
ሳይጫወቱ በጠራው ሰማይ ላይ ተንቀለቀሉበት፡፡ በተለይ ፀሐይ በየቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ሙሉ እየነደደች የወሎን ምድር ታነደውና ታቃጥለው ጀመር።ወንዞች ነጠፉ። ሳር ቅጠሉ ደረቀ። ዛፎች ወደ ጭራሮነት ተቀየሩ። ቢመጣ ንፋስ ቢነሳ አቧራ ብቻ ሆነ።
የወሎ ገበሬ የመጀመሪያውን የድርቅ ዓመት ቀድሞ የነበረውን ጥሪት ተጠቅሞ ሳይደናገጥ ተወጥቶት ነበር። የሁለተኛው ግን ወገቡን ሰበረው፡፡ ሶስተኛው ደግሞ ከሥሩ ነቀለው፡፡ እንኳን ለራሱ ለሰንጋ ፈረሱ የእህል ዓይነት ይመርጥ እንዳልነበረ ሁሉ እንኳን ያቀምሰው የሚቀምሰውም አጣ፡፡ በሰንጋ ፈረስ ይጋልብ የነበረ የወሎ መኳንንት፤ በሲናር በቅሎ ስትፈስ የነበረች የወሎ ወይዛዝርት ሁሉ እርካባቸው ወለቀ። ግላሳቸው ተጠቀለለ። በቅሎና ፈረሶቻቸው የአውሬና የአዕዋፍ
ሲሳይ ሆኑ። አጥንቶቻቸው ሜዳ ሙሉ ተረጩ። የረገመው ሳይታወቅ ወሎ ምዕዓት ወረደበት። የረሀብ እሳት ያቃጥለው ጀመር፡፡ በቸነፈር ተመታ።
በዚያን ጊዜ፣ በዚያን ዘመን፣ የወሎ ሕዝብ ምርጫው አንድ ብቻ ነበር፤ ስደት። አቅጣጫው ደግሞ ወደ ደሴ ከተማ፡፡ ይህም ምክንያት ነበረው፡፡ የወቅቱ
ንጉሥ ለጉብኝት ደሴ ከተማ እንደሚገቡ ተወርቶ ነበር፡፡ እሳቸው ደግሞ በሄዱበት ሁሉ ለልጆች ከረሜላ በመርጨታቸው ብቻ የቸርነት ዝናን ያተረፉ ነበሩና
የወሎ ርሃብተኛ ወደ «ቸሩ» ንጉስ በመሄድ የልመና እጁቹን ለመዘርጋት ዳር አስከዳር ተነጋግሮ ወደ ደሴ መጓዝ መትመም ጀመረ።
ከሰሜን አቅጣጫ የራያና የየጁ ሕዝብ በርሀብ የመነመነ ሰውነቱን
ብጥቅጣቂ ጨርቅ እየሸፈነ ሰንሰለት ሰርቶ ወደ ደሴ ሲግተለተል የአንባሰል ተራሮች ቁልቁል እየተመለከቱ ይታዘቡ ነበር፡፡ ከምዕራብና ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ የቦረና! የወረሂመኖ፣ የሳስታና የወገልጤና ሕዝብ ተነቅንቆ ወደ ደሴ ሲጓን በመሀል እየደከመው በገሪዶና በቦሩ ሜዳ ላይ ሲፈስ የጦሳ ተራራ መዓል ላይ ቆሞ ግራና ቀኝ እየተመለከተ ያለቅስ ነበር፡፡ ከምስራቅና ከደቡብ ምሥራቅ
ደግሞ የአውሳ የቃሎ፣ የእንቻሮና የከሚሴ ሕዝብ በበረሃ አለባበስ ዘይቤው ከወገብ በታች ሽርጥ መሳይ አገልድሞ ከወገቡ በላይ ሲያዩት ግጠው ግጠው የጣሉት
አጥንት መስሎ ወደ ደሴ ሲተምም የቦርከና ወንዝ «እናንተስ ወደ ንጉሳችሁ ሄዳችሁ፤ የእኔንስ ችግር ለአባይና ለተከዜ ማን ይንገርልኝ»
እያለ የሚያዝን ይመስል ነበር፡፡
በጋ ከክረምት የውሃ ፈረሰኛ ሲያጓራበት እንዳልነበረ ሁሉ ያኔ ግን ክው ብሎ ደርቋልና በውስጡ የነበሩ ቋጥኛች ጨው መስለው የፀሐይ ንዳድ እየፈነከታቸው ነበር፡፡
ያ ሁሉ የወሎ ርሀብተኛ በዚህ መልክ ተጉዞ ተጉዞ ደሴ ከተማ ሲደርስ ያሰበው አልሆነለትም። እንዲያውም ወደ መሀል ደሴ ከተማ መግባት እንኳ ሳይፈቀድለት ቀረ። የንጉሡ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊሶች በየመጣበት አቅጣጫ ተሰልፈው ጠበቁት። ከስሜን በኩል የመጣውን በሮቢት ገበያ ላይ፣ ከምዕራብ በኩል የመጣውን ከሰኞ ገበያ ላይ እንዲሁም ከምስራቅና ደቡብ ምስራቅ እቅጣጫ የመጣውን
ርሀብተኛ ሀረጎ አፋፍ ላይ በተሰራ የእንጨት አጥር ውስጥ እያስገቡ አጎሩት። በቀን አንዳንድ ዳቦ ለእያንዳንዱ ርሀብተኛ እንደ ውሻ ይጥሉለት ጀመር፡፡ እንዳይነቃነቅ ይጠብቁትም ጀመር።
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ይደልዎ ይደልዎ”
ምንትዋብ፣ ኢያሱ በነገሠ በሁለተኛው ወር ረጅም ነጭ ሐር ቀሚስ ለብሳ፣ በወርቅና በዕንቁ የተንቆጠቆጠ ካባ በላዩ ላይ ደርባ፣ በወርቅ አጊጣ፣ ፊቷን በነጭ ዐይነ ርግብ ከልላ፣ የወርቅ በትረ መንግሥት ጨብጣና ከወርቅ የተሠራ ነጠላ ጫማ ተጫምታ ተሸልማ በወጣችው
በቅሎዋ ላይ ተሰይማ፣ የንግሥ ሥርዐት ወደሚፈጸምበት ወደ መናገሻ ግንብ አመራች።
መናገሻ ግንብ ውስጥ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ አዛዦች፣ ካህናት፣ ሊቃውንትና ወይዛዝርት
እንደየማዕረጋቸው ቦታቸውን ይዘው የንጉሥ መሞት የሚያመጣውን ቀውስ ጠንቅቃ
የምታውቀው ምንትዋብ፣ አክሱም ጽዮን የሚደረገውን ሁለተኛውን
የኢያሱን የንግሥ ሥርዐት አስቀርታ በነገሠ በወሩ ብርሃን ሰገድ የሚል ስመ መንግሥት ከተሰጠው ከዳግማዊ ኢያሱና ከቤተሰቦቿ ጋር ስትገባ ሁሉ ተነሥቶ እጅ ነሳ።
በወርቅ ያጌጠውን የአባቱን ዘውድ የጫነውና የእሳቸውን የወርቅ
በትረ መንግሥት የጨበጠው ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “እናቴን አንግሡልኝ፣ መንግሥቴ ያለሷ አይጠናም” ሲል ተሰብሳቢዎቹ፣ “ይደልዎ ይደልዎ! ይገባታል! ይገባታል! ጎበዝ ክርስቲያን፣ አዋቂ ናት። ሽህ ዓመት ንገሥ። የቆስጦንጢኖስን ምሽት
እሌኒን ትመስላታለች” አሉ።
አንጋሹ ጽራግ ማሰሬ ማሞ ከዕንቁ፣ ከወርቅና ከብር የተሠራውንና በሻሽ ተሸፍኖ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠውን የአፄ ሚናስ የነበረውን ዘውድ አንስተው ምንትዋብ ራስ ላይ ጭነውላት ሲያበቁ ዝቅ ብለው ሰገዱላት፣ ከኢያሱ ቀኝም አስቀመጧት።
ባራኪው እልፍዮስ፣ “እዝጊሃር ክፉዎችን እንዲያሸንፉ ኃይል ይስጥዎ። ክብርዎን ያብዛልዎ። ፈሪሐ እዝጊሃርን በልብዎ ያሳድርልዎ። አቤቱ አምላካችን ሆይ! በአገልጋይህ በእቴጌ ምንትዋብ ላይ እኼን የደስታና
የክብር ዘውድ አኑር፤ እኼውም የቸርነት፣ የርህራሄ፣ የዕውቀትና የጥበብ ዘውድ ይሁንላቸው” ብሎ ሲባርካት፣ ከኋላዋ ቆመው የነበሩት ሴት የመሣፍንት ዘሮችና ወይዛዝርት ዕልልታውን አቀለጡት።
ምንትዋብ ለአምላኳ በልቧ ምስጋና አቀረበች።
ካህናት ዘመሩ፣ ወረቡ፣ ሊቃውንቱ ቅኔ አወረዱ። እንደ ንግሥተ
ሳባ፣ እቴጌ እሌኒ፣ እቴጌ ሰብለወንጌልና እቴጌ መስቀል ክብራን የመሳሰሉ የታላላቅ ሴቶች ስም እየጠቀሱ አሞካሿት። “አንቺ እሌኒ ማለት ነሽ። ልዥሸን ብርሃን ሰገድ ኢያሱን ኸጎኑ ሁነሽ እንደምትረጂው አንጠራጠርም” ሲሉ እሷ ላይ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገለፁላት።
ምንትዋብ፣ አባቷ ዕጣ ፈንታ፣ እናቷ ዕድል አያቷ ግን የተገባት ያሉትን ስትጎናፀፍ ተስተዋለ።
ሕይወት ሲሻት ለጋሥ መሆኗን አስመሰከረች።
ባለ ክራሩና ባለ መሰንቆው የውዳሴና የሙገሳ ግጥም ሲያንቆረቁር፣ፎካሪው በቀረርቶ፣ ሽላዩ በሽለላ የበኩሉን ምስጋና አበረከተ። አንዱ ሀሚና ተነሰቶ በመሰንቆ፣
በወለተጴጥሮስ ተወልዳ በንግርት፣
በእዝጊሄር ፈቃድ በነብያት ትንቢት፤
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ያገራችን ውበት፤
የምታስተባብር ጥድቅ ተሃይማኖት፣
ዳር ድንበር ጠባቂ ያባቶቿን ርስት፣
ኸዝኸ በላይ ጠጋ ኻአምላክ መሰጠት፣
ምንድን ሊሰጧት ነው ምንትዋብ ሚሏት?
እያለ ሲያሞግሳት፣ የተሰበሰበው ሰው ደግሞ እሱን አመሰገነው።
ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መለከት እየተነፋ ከመናገሻ ግንብ በደጅ
አጋፋሪው አቀናባሪነት የፊቱን ወጀብ ሰንደቅ የያዙ፣ የእልፍኝ አሽከሮች፣ባለሟሎችና ሠይፈ ጃግሬዎች ፈንጠር ብለው እየመሩ፣ የመሃል ዐጀቡ
በእልፍኝ አስከልካዩ እየተጠበቀ፣ ኢያሱና ምንትዋብ ጎን ለጎን ሆነው
ድባብ ተይዞላቸው፣ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ ሊቃውንት፣ ወይዛዝርት፣ግራዝማቾች፣ ቀኛዝማቾችና የጦር አበጋዞች እንደየደረጃቸው ከኋላ
እያጀቧቸው፣ ሰልፍ አስከባሪዎቹና የንጉሠ ነገሥቱ ጠባቂ የሆኑት ጋሻዐጃግሬዎቹ ተከትለው የሰልፉን ግራና ቀኝ አንጋቾች እየጠበቁ ራስ ቢትወደዱ በመጨረሻ ተሰልፈው ነገሥታቱ በዘፈንና በጭፈራ ከግቢ
ሲወጡ ካህናት፣
መንክር ግርማ መንክር ግርማ
ወልደልዑል ጸለላ መንክር ግርማ
የምትደንቅ ግርማ ሞገስን
የምትደንቅ ግርማ ሞገስ
የወልደልዑል ልጅ፣ እጅግ የላቀው አባት ልጅ፤
እያሉ፣ ምንትዋብ በወንድሟ በወልደልዑል መከታነት መንገሧን
በቅኔ ጠቅ እያደረጉ በፀናፅልና በከበሮ ዐጀቧት።
ዘውዷን እንደጫነች በቅሎዋ ላይ ተሰይማና ታጅባ፣ ወደ ሕዝቡ
አመራች። ከጐንደርና ከአካባቢዋ የመጣው ነፍጠኛ፣ ገበሬ፣ እረኛ፣
ነጋዴ፣ ወታደር፣ አንጥረኛ፣ ሸማኔ፣ ቆዳ አልፊ፣ ጥልፍ ጠላፊ፣ ሹሩባ ሠሪ መድኃኒት አዋቂ፣ ወጌሻ፣ የቤት እመቤት፣ አረቄና ጠላ ሻጭ፣ ዲያቆን ተማሪ ፣ የቁም ጸሐፊ፣ ሠዓሊ፣ ብራና ሠሪ፣ ባለክራሩና ባለመሰንቆው
ሴቱ ሹሩባውን አንዠርጎ፣ ነጠላውን አጣፍቶ፣ ወገቡን በድግ ደግፎ ማተቡ ላይ የእንጨት መስቀሉን፣ ድሪውን፣ ጨሌውን፣ ዶቃውን ቁርጭምጭሚቱ ዙርያ አልቦውን፣ የእጁ አንጓ ላይ አንባሩን ደርድሮ ገሚሱ የቀርከሀ ጃንጥላውን አጥልቶ፣ ወንዱ ፀጉሩን አጎፍሮ፣ ለምዱን ደርቦ፣ ዱላውን ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ፣ ልጆች ጥብቋቸውን
አጥልቀው፣ ክታባቸውን አንጠልጥለው ምንትዋብ ከኢያሱ ጋር ጃን ተከል ብቅ ስትል አካባቢው ድብልቅልቁ ወጣ።
ሴቶች በዕልልታና በእስክስታ፣ ወንዶች በሆታና በጭፈራ አካባቢውን አናጉት፤ ካህናት በሽብሸባ አደመቁት። እነምንትዋብ ካለፉ በኋላ፣
ሕዝቡ መስመሩን ተከትሎ እየሮጠ ዕልል! ሆ! እያለ ዐጀባቸው።
ጐንደሬዎች እንደዛ ውበት የነገሠበት ሰው አይተው አያውቁምና በምንትዋብ ውበት ተደመሙ። “አቤት መልኳ እንደ ጠሐይ ሚያበራ አቤት ወርቅ አካል!” እያሉ ተደነቁ። በደስታ ተሳክረው ለአፄ ፋሲለደስ፣
አሁን ወጣ ጀንበር
ተደብቆ ነበር
ተብሎ እንደተዘፈነው ሁሉ ለእርሷም፣
አሁን ወጣች ጀንበር
ተሸሽጋ ነበር
እያሉ አዜሙ፤ ጨፈሩ።
አሁን ወጣች ጨረቃ፣
የምትለን ፍርድ ይብቃ።
ደስ ይበልህ ዘመድ፣
ከነገሠች በዘውድ።
ደስ ይበልሽ ወይዘሮ፣
ጭና መጣች ወገሮ።
ደስ ይበልህ ባለእጌ፤
ነገሠች እቴጌ።
ደስ ይበልህ ጐንደር፤
ቀድሞ ከፍቶህ ነበር፣
ሲሉ ጐንደሬዎች ለውዷ ከተማቸው መልካሙን ተመኙላት።
ምንትዋብ የተስፋ ጨረር ፈነጠቀችላቸው።
ዐዲስ ንጉሥ በመጣ ቁጥር የተስፋ ስንቅ ሰንቆ የሚወጣው
መልካሙን ተመኘ ለጦርነት ሳይዳረግ፣ በወታደር ሳይዘረፍ፣ ሚስቱና ልጁ ሳይደፈሩ እኖራለሁ በሚል ተስፋ፣ ከትናንቱ ዛሬ ይሻለኝ ይሆን በሚል ምኞት።
ጐንደሬዎች ምንትዋብን ወደዷት፤ ቀልቧ ገዛቸው፤ መልኳ
አባበላቸው፤ ግርማ ሞገሷ ማረካቸው፣ ኩራታቸው በእሷ ሆነ። በዓለ ንግሥናዋን አደመቁላት፤ ዐደራቸውን ሰጧት፤ ተስፋቸውን ልባቸው ጫፍ ላይ አንጠልጥለው ፎከሩላት፤ ሽለሉላት፤ ዘፈኑላት፤ ጨፈሩላት፤
ዕልል! ሆ! አሉላት።
ጥላዬ፣ ከእነአብርሃ ጋር ከካህናቱ ኋላ ሆኖ አብሮ እየዘመረ ሲሄድ
ድንገት ምንትዋብን ከኢያሱ ጋር አያት። የለበሰችው ነጭ ሐር ቀሚስ፣ፊቷን የጋረደው ነጭ ዐይነርግብ ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዐይኑ ላይ አንፀባረቀበት። ያየውን ሁሉ ማመን አቃተው። የባሏ ለቅሶ ላይ አዝኖላት እንባውን እንደረጨላት ሁሉ አሁን የያዘውን የደስታ ሲቃ መቆጣጠር አቃተው። እንባው ፊቱን አራሰው። እነአብርሃ እንባውን እንዳያዩበት በሰዉ መሃል ተሸለክልኮ ወጥቶ “ኸንግዲህ ደብረ ወርቅ ብመለስም አይቆጨኝ” ብሎ ወደ ቤት ሄደ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“ይደልዎ ይደልዎ”
ምንትዋብ፣ ኢያሱ በነገሠ በሁለተኛው ወር ረጅም ነጭ ሐር ቀሚስ ለብሳ፣ በወርቅና በዕንቁ የተንቆጠቆጠ ካባ በላዩ ላይ ደርባ፣ በወርቅ አጊጣ፣ ፊቷን በነጭ ዐይነ ርግብ ከልላ፣ የወርቅ በትረ መንግሥት ጨብጣና ከወርቅ የተሠራ ነጠላ ጫማ ተጫምታ ተሸልማ በወጣችው
በቅሎዋ ላይ ተሰይማ፣ የንግሥ ሥርዐት ወደሚፈጸምበት ወደ መናገሻ ግንብ አመራች።
መናገሻ ግንብ ውስጥ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ አዛዦች፣ ካህናት፣ ሊቃውንትና ወይዛዝርት
እንደየማዕረጋቸው ቦታቸውን ይዘው የንጉሥ መሞት የሚያመጣውን ቀውስ ጠንቅቃ
የምታውቀው ምንትዋብ፣ አክሱም ጽዮን የሚደረገውን ሁለተኛውን
የኢያሱን የንግሥ ሥርዐት አስቀርታ በነገሠ በወሩ ብርሃን ሰገድ የሚል ስመ መንግሥት ከተሰጠው ከዳግማዊ ኢያሱና ከቤተሰቦቿ ጋር ስትገባ ሁሉ ተነሥቶ እጅ ነሳ።
በወርቅ ያጌጠውን የአባቱን ዘውድ የጫነውና የእሳቸውን የወርቅ
በትረ መንግሥት የጨበጠው ብርሃን ሰገድ ኢያሱ ከተቀመጠበት ተነስቶ፣ “እናቴን አንግሡልኝ፣ መንግሥቴ ያለሷ አይጠናም” ሲል ተሰብሳቢዎቹ፣ “ይደልዎ ይደልዎ! ይገባታል! ይገባታል! ጎበዝ ክርስቲያን፣ አዋቂ ናት። ሽህ ዓመት ንገሥ። የቆስጦንጢኖስን ምሽት
እሌኒን ትመስላታለች” አሉ።
አንጋሹ ጽራግ ማሰሬ ማሞ ከዕንቁ፣ ከወርቅና ከብር የተሠራውንና በሻሽ ተሸፍኖ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠውን የአፄ ሚናስ የነበረውን ዘውድ አንስተው ምንትዋብ ራስ ላይ ጭነውላት ሲያበቁ ዝቅ ብለው ሰገዱላት፣ ከኢያሱ ቀኝም አስቀመጧት።
ባራኪው እልፍዮስ፣ “እዝጊሃር ክፉዎችን እንዲያሸንፉ ኃይል ይስጥዎ። ክብርዎን ያብዛልዎ። ፈሪሐ እዝጊሃርን በልብዎ ያሳድርልዎ። አቤቱ አምላካችን ሆይ! በአገልጋይህ በእቴጌ ምንትዋብ ላይ እኼን የደስታና
የክብር ዘውድ አኑር፤ እኼውም የቸርነት፣ የርህራሄ፣ የዕውቀትና የጥበብ ዘውድ ይሁንላቸው” ብሎ ሲባርካት፣ ከኋላዋ ቆመው የነበሩት ሴት የመሣፍንት ዘሮችና ወይዛዝርት ዕልልታውን አቀለጡት።
ምንትዋብ ለአምላኳ በልቧ ምስጋና አቀረበች።
ካህናት ዘመሩ፣ ወረቡ፣ ሊቃውንቱ ቅኔ አወረዱ። እንደ ንግሥተ
ሳባ፣ እቴጌ እሌኒ፣ እቴጌ ሰብለወንጌልና እቴጌ መስቀል ክብራን የመሳሰሉ የታላላቅ ሴቶች ስም እየጠቀሱ አሞካሿት። “አንቺ እሌኒ ማለት ነሽ። ልዥሸን ብርሃን ሰገድ ኢያሱን ኸጎኑ ሁነሽ እንደምትረጂው አንጠራጠርም” ሲሉ እሷ ላይ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገለፁላት።
ምንትዋብ፣ አባቷ ዕጣ ፈንታ፣ እናቷ ዕድል አያቷ ግን የተገባት ያሉትን ስትጎናፀፍ ተስተዋለ።
ሕይወት ሲሻት ለጋሥ መሆኗን አስመሰከረች።
ባለ ክራሩና ባለ መሰንቆው የውዳሴና የሙገሳ ግጥም ሲያንቆረቁር፣ፎካሪው በቀረርቶ፣ ሽላዩ በሽለላ የበኩሉን ምስጋና አበረከተ። አንዱ ሀሚና ተነሰቶ በመሰንቆ፣
በወለተጴጥሮስ ተወልዳ በንግርት፣
በእዝጊሄር ፈቃድ በነብያት ትንቢት፤
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ያገራችን ውበት፤
የምታስተባብር ጥድቅ ተሃይማኖት፣
ዳር ድንበር ጠባቂ ያባቶቿን ርስት፣
ኸዝኸ በላይ ጠጋ ኻአምላክ መሰጠት፣
ምንድን ሊሰጧት ነው ምንትዋብ ሚሏት?
እያለ ሲያሞግሳት፣ የተሰበሰበው ሰው ደግሞ እሱን አመሰገነው።
ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መለከት እየተነፋ ከመናገሻ ግንብ በደጅ
አጋፋሪው አቀናባሪነት የፊቱን ወጀብ ሰንደቅ የያዙ፣ የእልፍኝ አሽከሮች፣ባለሟሎችና ሠይፈ ጃግሬዎች ፈንጠር ብለው እየመሩ፣ የመሃል ዐጀቡ
በእልፍኝ አስከልካዩ እየተጠበቀ፣ ኢያሱና ምንትዋብ ጎን ለጎን ሆነው
ድባብ ተይዞላቸው፣ መሣፍንት፣ መኳንንት፣ ሊቃውንት፣ ወይዛዝርት፣ግራዝማቾች፣ ቀኛዝማቾችና የጦር አበጋዞች እንደየደረጃቸው ከኋላ
እያጀቧቸው፣ ሰልፍ አስከባሪዎቹና የንጉሠ ነገሥቱ ጠባቂ የሆኑት ጋሻዐጃግሬዎቹ ተከትለው የሰልፉን ግራና ቀኝ አንጋቾች እየጠበቁ ራስ ቢትወደዱ በመጨረሻ ተሰልፈው ነገሥታቱ በዘፈንና በጭፈራ ከግቢ
ሲወጡ ካህናት፣
መንክር ግርማ መንክር ግርማ
ወልደልዑል ጸለላ መንክር ግርማ
የምትደንቅ ግርማ ሞገስን
የምትደንቅ ግርማ ሞገስ
የወልደልዑል ልጅ፣ እጅግ የላቀው አባት ልጅ፤
እያሉ፣ ምንትዋብ በወንድሟ በወልደልዑል መከታነት መንገሧን
በቅኔ ጠቅ እያደረጉ በፀናፅልና በከበሮ ዐጀቧት።
ዘውዷን እንደጫነች በቅሎዋ ላይ ተሰይማና ታጅባ፣ ወደ ሕዝቡ
አመራች። ከጐንደርና ከአካባቢዋ የመጣው ነፍጠኛ፣ ገበሬ፣ እረኛ፣
ነጋዴ፣ ወታደር፣ አንጥረኛ፣ ሸማኔ፣ ቆዳ አልፊ፣ ጥልፍ ጠላፊ፣ ሹሩባ ሠሪ መድኃኒት አዋቂ፣ ወጌሻ፣ የቤት እመቤት፣ አረቄና ጠላ ሻጭ፣ ዲያቆን ተማሪ ፣ የቁም ጸሐፊ፣ ሠዓሊ፣ ብራና ሠሪ፣ ባለክራሩና ባለመሰንቆው
ሴቱ ሹሩባውን አንዠርጎ፣ ነጠላውን አጣፍቶ፣ ወገቡን በድግ ደግፎ ማተቡ ላይ የእንጨት መስቀሉን፣ ድሪውን፣ ጨሌውን፣ ዶቃውን ቁርጭምጭሚቱ ዙርያ አልቦውን፣ የእጁ አንጓ ላይ አንባሩን ደርድሮ ገሚሱ የቀርከሀ ጃንጥላውን አጥልቶ፣ ወንዱ ፀጉሩን አጎፍሮ፣ ለምዱን ደርቦ፣ ዱላውን ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ፣ ልጆች ጥብቋቸውን
አጥልቀው፣ ክታባቸውን አንጠልጥለው ምንትዋብ ከኢያሱ ጋር ጃን ተከል ብቅ ስትል አካባቢው ድብልቅልቁ ወጣ።
ሴቶች በዕልልታና በእስክስታ፣ ወንዶች በሆታና በጭፈራ አካባቢውን አናጉት፤ ካህናት በሽብሸባ አደመቁት። እነምንትዋብ ካለፉ በኋላ፣
ሕዝቡ መስመሩን ተከትሎ እየሮጠ ዕልል! ሆ! እያለ ዐጀባቸው።
ጐንደሬዎች እንደዛ ውበት የነገሠበት ሰው አይተው አያውቁምና በምንትዋብ ውበት ተደመሙ። “አቤት መልኳ እንደ ጠሐይ ሚያበራ አቤት ወርቅ አካል!” እያሉ ተደነቁ። በደስታ ተሳክረው ለአፄ ፋሲለደስ፣
አሁን ወጣ ጀንበር
ተደብቆ ነበር
ተብሎ እንደተዘፈነው ሁሉ ለእርሷም፣
አሁን ወጣች ጀንበር
ተሸሽጋ ነበር
እያሉ አዜሙ፤ ጨፈሩ።
አሁን ወጣች ጨረቃ፣
የምትለን ፍርድ ይብቃ።
ደስ ይበልህ ዘመድ፣
ከነገሠች በዘውድ።
ደስ ይበልሽ ወይዘሮ፣
ጭና መጣች ወገሮ።
ደስ ይበልህ ባለእጌ፤
ነገሠች እቴጌ።
ደስ ይበልህ ጐንደር፤
ቀድሞ ከፍቶህ ነበር፣
ሲሉ ጐንደሬዎች ለውዷ ከተማቸው መልካሙን ተመኙላት።
ምንትዋብ የተስፋ ጨረር ፈነጠቀችላቸው።
ዐዲስ ንጉሥ በመጣ ቁጥር የተስፋ ስንቅ ሰንቆ የሚወጣው
መልካሙን ተመኘ ለጦርነት ሳይዳረግ፣ በወታደር ሳይዘረፍ፣ ሚስቱና ልጁ ሳይደፈሩ እኖራለሁ በሚል ተስፋ፣ ከትናንቱ ዛሬ ይሻለኝ ይሆን በሚል ምኞት።
ጐንደሬዎች ምንትዋብን ወደዷት፤ ቀልቧ ገዛቸው፤ መልኳ
አባበላቸው፤ ግርማ ሞገሷ ማረካቸው፣ ኩራታቸው በእሷ ሆነ። በዓለ ንግሥናዋን አደመቁላት፤ ዐደራቸውን ሰጧት፤ ተስፋቸውን ልባቸው ጫፍ ላይ አንጠልጥለው ፎከሩላት፤ ሽለሉላት፤ ዘፈኑላት፤ ጨፈሩላት፤
ዕልል! ሆ! አሉላት።
ጥላዬ፣ ከእነአብርሃ ጋር ከካህናቱ ኋላ ሆኖ አብሮ እየዘመረ ሲሄድ
ድንገት ምንትዋብን ከኢያሱ ጋር አያት። የለበሰችው ነጭ ሐር ቀሚስ፣ፊቷን የጋረደው ነጭ ዐይነርግብ ከፀሐይዋ ብርሃን ጋር ተደምሮ ዐይኑ ላይ አንፀባረቀበት። ያየውን ሁሉ ማመን አቃተው። የባሏ ለቅሶ ላይ አዝኖላት እንባውን እንደረጨላት ሁሉ አሁን የያዘውን የደስታ ሲቃ መቆጣጠር አቃተው። እንባው ፊቱን አራሰው። እነአብርሃ እንባውን እንዳያዩበት በሰዉ መሃል ተሸለክልኮ ወጥቶ “ኸንግዲህ ደብረ ወርቅ ብመለስም አይቆጨኝ” ብሎ ወደ ቤት ሄደ።
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
በሰፊ ውብ አፏ እየሳቀችብኝ፡ እየወደደችኝ ድንገት ሳቁን እየተወች አንድ ነገር ልነግርህ እፈልግ ነበር» አለችኝ ንገሪኝ
እንዳትቆጣ፡፡ ወንድ ሆነህ አትስማኝ፡ ደራሲ ሆነህ አዳምጠኝ እንጂ
«እሺ»
"Parole d'honneur?"
"Parole d'honneur!"
«አንተን እወድሀለሁ። ከልቤ አፈቅርሀለሁ፡፡ ግን ፖልን ልረሳው
አልችልም። የመጀመሪያዬ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን፣ ሳልጠግበው
ስለሄደብኝ ጭምር ይመስለኛል። «ይገባሀል?»
«ይገባኛል»
«እና አንድንድ ጊዜ ይናፍቀኛል፡፡ ይመስለኛል፣ በውስጤ
የልጃገረድነቴ ጊዜያት ከሱ ጋር ተዋህዷል፡፡ እና ያ ጊዜያት
ሲናፍቀኝ፣ ፖል ይናፍቀኛል። ከልቤ ላወጣው ልረሳው እሞክራለሁ።
ግን የምችል አይመስለኝም፡፡ የምልህ ይገባሀል?»
«ይመስለኛል»
«ስለዚህ ፖልን የሚመስል ሰው ሁሉ ደስ ይለኛል፤ ይስበኛል።
... እና ስለ ባህራም ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡»
ይናገራል ብላ ዝም አለች። መናገሩ እየከበዳት ሄዷል። ዝም
ብዬ ሳያት ቀጠለች
«አንተ ነህ ባህራምን እንድወደው ያረግከኝ፡፡ ስለሱ ብዙ ብዙ
አወራህልኝ። አራት ወር ሙሉ አወራህልኝ፡፡ ከወሬህ እንዳየሁት፣
በጣም በጣም ታከብረዋለህ። ግን እንደማውቅህ አንተ ማንንም
አታከብርም፡፡ ስለዚህ፣ ይሄ ባህራም እንዴት ያለ ሰው ቢሆን ነው? አልኩ። አንዲት ሴት እንዲህ ካለች ደሞ መመለሻ የላትም። ይህን ያባሰው ምንድነው? ከወሬህ እንደተገነዘብኩት ባህራም እንደ ፖል ያለ ሰው ነው። እንደሌላው ሰው ከተራ ጭቃ ተጠፍጥፎ አልተሰራም፡፡ ጀግናዎቹ ከሚሰሩበት ከልዩ ጭቃ ተቀርፆ፣ በልዩ ንፁህ እሳት ውስጥ ነው የተጠበሰው። ባህራምን እንደዚህ አድርገህ
ነው ያሳየኸኝ
«አንተ ያንን ያህል እያከበርከው፣ ከፖል ጋር ያንን ያህል
እየተመሳሰለ፣ እንዴት ላይለኝ ይችላል? እኔ ደሞ
እንደምታውቀኝ ነኝ:: እንዴት ላልመኘው እችላለሁ?»
«ፍቅር ይዞሻል?»
ራሷን በሀይል
እየነቀነቀች፡ ከኋላዋ ጥቁር ሀር ፀጉሯ እየተወዛወዘ፣ የደስታ ሳይሆን የመሰቃየትና የመደናገር ፈገግታ ውብ አፏን እየሸመቀቀው
እኔ እንጂ! እኔ እንጃ! እኔ እንጃ!» አለችና ራሷን ጠረጴዛው ላይ
ደፋች
ረዥም ፀጥታ
እጄን ሰድጄ ራሷ ላይ አሳረፍኩት። ቀና ብላ አየችኝ፡፡ እምባዋ
ይወርዳል
«ሶስት ፍቅር አንድ ላይ ሊይዝ ይችላል?» አለችኝ
“ሴትዮዋ ተራ ከሆነች አይችልም» አልኳት
ጠረጴዛው ላይ የነበረ እጄን ወስዳ ከጎንጯ ጋር እያተሻሸት፣
በእምባዋ እጄን እያረጠበች፡ በተጨነቀ ድምፅ
«ብዙ ጎዳሁህ፣ የኔ ቢራቢሮ?» አለችኝ
ግድ የለሽም አልኳት
«አለኝ እንጂ። ላንተ ብዙ ግድ አለኝ፡፡ ለዚህ እኮ ነው
የምነግርህ፡፡»
«አውቃለሁ»
ለኔ እንዴት ጥሩ ነህ! አሁን ምን ይሻለኛል?»
ቆንጆ ነሽ። ተወዳጅ ነሽ፡፡ ለምን አትወጂውም?»
በመሀረቤ እምባዋን እየጠረገች
«አንተስ? አትቀየምም?»
ሌሎች ጋ ትሂጂ የለ? ስለዚህ ለኔ ያው ነው»
ውይ! እንዴት ደግ ነህ!?»
«ለምን?»
ውሸትክን ነዋ» ተናፈጠች
እኔ እንድደሰት ብለህ
ትሰቃያለህ፡፡»
«የምን ስቃይ?»
መሀረቤን አጥፋ እየመለሰችልኝ
«እንግዲህ አትዋሽ። ይበቃሀል። አውቅሀለሁ'ኮ። ከምትገምተው
በላይ አውቅሀለሁ፡፡ ፊትህ ላይና አይኖችህ ውስጥ ስንትና ስንት ነገር ይታየኛል መስለህ።»
«ምን ይታይሻል?»
«ስለባህራም ስነግርህ በብዙ ነው ያዘንከው::
«ላንቺ ነዋ ያዘንኩልሽ፡፡
«እሱም ታይቶኛል። ግን ለራስህም በሀይል በመሰቃየት ላይ ነህ፡፡ እና በጣም አዝናለሁ፡፡ እንዲህ በመሆኔ በጣም አዝናለሁ፡፡»
«በማዘን የትም አይደረስም፡፡»
አውቃለሁ የኔ ቆንጆ:: ግን ማዘን አይቀርም፡፡»
ዝም ዝም ሆነ
«በኔ ብቻ ሳይሆን በባህራምም ጭምር ነው ያዘንከው። ልክ
ዝም አልኳት
«እንግዲህ ልንገርህ፡፡ እውነቱን ብታውቅ ይሻላል። ልንገርህ?»
«እሺ፡፡»
«ያን እለት ማታ ያ ሰውዬ ባህራምን ሊገድለው አልመጣም?
እና አንተ ኒኮልን ይዘህ ማርዕይ አልሄድክም? ከኒኮል ጋር
ምንም አልሰራችሁም? እውነት ተናገር፡፡»
«ምንም አልሰራንም፡፡ ይልቅ ቀጥዪ።»
«እና ሰውየውን ሲገድለው አላየሁም? እሱን ነግሬሀለሁ። እና
ከዚያ ወደ ቤት ሄድን፡፡ ባህራም ልክ ምንም እንዳልስራ በእርጋታ
ሶፋ ላይ ተቀመጠ። እኔ መጠጥ ሰጠሁትና ሶፋው ላይ አልጋ ብጤ
አነጠፍኩለት፡፡ አንጥፌ ስጨርስ 'እንግዲህ እዚህ ውስጥ ይተኛል።
ነብስ ገድሏል፤ ግን እዚህ ውስጥ ይተኛል። ከጀግና ጋር ነው'ኮ
ያለሁት። ከነብሰ ገዳይ ጋር ነው ያለሁት ብዬ አሰብኩ፡፡ ዘወር ብዬ
አየሁት። አንተ እንደ ነገርከኝ ነው። ዝም ሲል የኢራንን ሻህ
ይመስላል። ግን ማን ያውቃል? ጀግና ስለሆነ አንድ ቀን የኢራንን
ሻህ ይገድለው ይሆናል'ኮ!' ብዬ አሰብኩ
«እና በሀይል ተመኘሁት፡፡ ፍትወት ያንን ያህል አንቆ ይዞኝ
አያውቅም፡፡ ራሴን 'ተይ እንደሱ አታርጊ! - ተይ!'
እያልኩ
ከተቀመጠበት ሄድኩና እግሩ አጠገብ ተምበርክኬ ወደላይ አየሁት።
እንደ ቄስ እጁን ራሴ ላይ አሳረፈና
«ምን ሆነሻል?» አለኝ
ቀስ ብዬ ተነሳሁና አፉ ላይ ሳምኩት
አሁንም «ምን ሆነሻል?» አለኝ። ግን ገብቶታል
«ፈልጌሀለሁ» አልኩት
«እኔ አልፈልግሽም» አለ
«አውቃለሁ ትፈልገኛለህ፡፡ ትፈልገኝ የለ?»
«አዎን፡፡ ካየሁሽ ጀምሮ እንደፈለግኩሽ ነው::»
«ይኸዋ፡፡ አለሁልህ!»
«አይሆንም!»
«ለምን አይሆንም?»
«ምክንያቱን መቼ አጣሽው» አንተን ማለቱ ነው
«እሱ ንደሆነ ግድ የለውም» ኣልኩት
«እኔ ግድ አለኝ!»
«ለምን?»
«ጓደኛዬ ነው:: እፈልግሻለሁ፡፡ ግን እሺ አልልሽም። ስለዚህ
እርሺው!»
«አልረሳውም፡፡ ልረሳው አልችልም፡፡ ልረሳው አልፈልግም።
ሌሊት እመጣለሁ!» አልኩትና ሄጄ አልጋዬ ውስጥ ገባሁ፡፡ ልተወው
ቆረጥኩ። ምናልባት አንድ ሰአት ያህል ቆየሁ። ከዚያ በላይ ግን
ልቆይ አልቻልኩም፡፡ እንደዚህ አላስችል ያለኝ እሱ ስለሆነ ብቻ
ነበር፣ ወይስ ሰው ሲገድል ስላየሁት ነበር? አላውቅም፡፡ የሆነ ሆኖ፣ እሱ እዚያ ተጋድሞ እኔ እዚህ ሆኜ ልታገስ አልቻልኩም
ራቁቴን ወጣሁ፡፡ ሽቶ ተቀባሁ፡፡ ከመኝታዬ ወጣሁ፡፡ የንግዳ
ቤቱን መብራት አበራሁ። እንቅልፍ አልወሰደውም ነበር። በቀጥታ
ሄድኩና ከበላዩ ቆምኩ፡፡ ወደላይ አየኝ፡፡ ሲያየኝ ብዙ ጊዜ ቆየ፡፡
እጁን ሰደደ። ጭኔን ይዞ ወደታች ጎተተኝ
ካሸነፈኩት በኋላ ወደ አልጋዬ ሄድን፡፡»
ዝም አለች፡፡ ያችን ሌሊት እንደምታስታውስ ያስታውቃል፡፡
እንዴት ያለች ሌሊት ነበረች ይሆን? ብጠይቃት እንደማትነግረኝ
እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ስለሌሎቹ ወንዶች በሰፊው ትንገረኝ እንጂ፣
ስለነሱ ጥቃቅኑን ስጋዊ ተግባር ሳይቀር ትዘርዝርልኝ እንጂ፣
ስለፖልና ስለ ባሀራም አትነግረኝም፡፡ እኔም ስለነሱ መጠየቅ ልክ አልመሰለኝም፡፡ ዝም አልኩ። ቀጠለች
«ስለሌሊቱ ልንገርህ እንዴ?» አለችኝ
«ልትነግሪኝ ትፈልጊያለሽ?»
«አልፈልግም። ከፈለግክ ግን እነግርሀለሁ።»
ይህን ያለችኝ «ሳትፈልጊ ብትነግሪኝ ደስ አይለኝም»
እንደምላት አውቃ ነው እንጂ፡ ንገሪኝ ብላትም እንደማትነግረኝ
አውቃለሁ
«ሳትፈልጊ ብትነግሪኝ ደስ አይለኝም» አልኳት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
በሰፊ ውብ አፏ እየሳቀችብኝ፡ እየወደደችኝ ድንገት ሳቁን እየተወች አንድ ነገር ልነግርህ እፈልግ ነበር» አለችኝ ንገሪኝ
እንዳትቆጣ፡፡ ወንድ ሆነህ አትስማኝ፡ ደራሲ ሆነህ አዳምጠኝ እንጂ
«እሺ»
"Parole d'honneur?"
"Parole d'honneur!"
«አንተን እወድሀለሁ። ከልቤ አፈቅርሀለሁ፡፡ ግን ፖልን ልረሳው
አልችልም። የመጀመሪያዬ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን፣ ሳልጠግበው
ስለሄደብኝ ጭምር ይመስለኛል። «ይገባሀል?»
«ይገባኛል»
«እና አንድንድ ጊዜ ይናፍቀኛል፡፡ ይመስለኛል፣ በውስጤ
የልጃገረድነቴ ጊዜያት ከሱ ጋር ተዋህዷል፡፡ እና ያ ጊዜያት
ሲናፍቀኝ፣ ፖል ይናፍቀኛል። ከልቤ ላወጣው ልረሳው እሞክራለሁ።
ግን የምችል አይመስለኝም፡፡ የምልህ ይገባሀል?»
«ይመስለኛል»
«ስለዚህ ፖልን የሚመስል ሰው ሁሉ ደስ ይለኛል፤ ይስበኛል።
... እና ስለ ባህራም ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡»
ይናገራል ብላ ዝም አለች። መናገሩ እየከበዳት ሄዷል። ዝም
ብዬ ሳያት ቀጠለች
«አንተ ነህ ባህራምን እንድወደው ያረግከኝ፡፡ ስለሱ ብዙ ብዙ
አወራህልኝ። አራት ወር ሙሉ አወራህልኝ፡፡ ከወሬህ እንዳየሁት፣
በጣም በጣም ታከብረዋለህ። ግን እንደማውቅህ አንተ ማንንም
አታከብርም፡፡ ስለዚህ፣ ይሄ ባህራም እንዴት ያለ ሰው ቢሆን ነው? አልኩ። አንዲት ሴት እንዲህ ካለች ደሞ መመለሻ የላትም። ይህን ያባሰው ምንድነው? ከወሬህ እንደተገነዘብኩት ባህራም እንደ ፖል ያለ ሰው ነው። እንደሌላው ሰው ከተራ ጭቃ ተጠፍጥፎ አልተሰራም፡፡ ጀግናዎቹ ከሚሰሩበት ከልዩ ጭቃ ተቀርፆ፣ በልዩ ንፁህ እሳት ውስጥ ነው የተጠበሰው። ባህራምን እንደዚህ አድርገህ
ነው ያሳየኸኝ
«አንተ ያንን ያህል እያከበርከው፣ ከፖል ጋር ያንን ያህል
እየተመሳሰለ፣ እንዴት ላይለኝ ይችላል? እኔ ደሞ
እንደምታውቀኝ ነኝ:: እንዴት ላልመኘው እችላለሁ?»
«ፍቅር ይዞሻል?»
ራሷን በሀይል
እየነቀነቀች፡ ከኋላዋ ጥቁር ሀር ፀጉሯ እየተወዛወዘ፣ የደስታ ሳይሆን የመሰቃየትና የመደናገር ፈገግታ ውብ አፏን እየሸመቀቀው
እኔ እንጂ! እኔ እንጃ! እኔ እንጃ!» አለችና ራሷን ጠረጴዛው ላይ
ደፋች
ረዥም ፀጥታ
እጄን ሰድጄ ራሷ ላይ አሳረፍኩት። ቀና ብላ አየችኝ፡፡ እምባዋ
ይወርዳል
«ሶስት ፍቅር አንድ ላይ ሊይዝ ይችላል?» አለችኝ
“ሴትዮዋ ተራ ከሆነች አይችልም» አልኳት
ጠረጴዛው ላይ የነበረ እጄን ወስዳ ከጎንጯ ጋር እያተሻሸት፣
በእምባዋ እጄን እያረጠበች፡ በተጨነቀ ድምፅ
«ብዙ ጎዳሁህ፣ የኔ ቢራቢሮ?» አለችኝ
ግድ የለሽም አልኳት
«አለኝ እንጂ። ላንተ ብዙ ግድ አለኝ፡፡ ለዚህ እኮ ነው
የምነግርህ፡፡»
«አውቃለሁ»
ለኔ እንዴት ጥሩ ነህ! አሁን ምን ይሻለኛል?»
ቆንጆ ነሽ። ተወዳጅ ነሽ፡፡ ለምን አትወጂውም?»
በመሀረቤ እምባዋን እየጠረገች
«አንተስ? አትቀየምም?»
ሌሎች ጋ ትሂጂ የለ? ስለዚህ ለኔ ያው ነው»
ውይ! እንዴት ደግ ነህ!?»
«ለምን?»
ውሸትክን ነዋ» ተናፈጠች
እኔ እንድደሰት ብለህ
ትሰቃያለህ፡፡»
«የምን ስቃይ?»
መሀረቤን አጥፋ እየመለሰችልኝ
«እንግዲህ አትዋሽ። ይበቃሀል። አውቅሀለሁ'ኮ። ከምትገምተው
በላይ አውቅሀለሁ፡፡ ፊትህ ላይና አይኖችህ ውስጥ ስንትና ስንት ነገር ይታየኛል መስለህ።»
«ምን ይታይሻል?»
«ስለባህራም ስነግርህ በብዙ ነው ያዘንከው::
«ላንቺ ነዋ ያዘንኩልሽ፡፡
«እሱም ታይቶኛል። ግን ለራስህም በሀይል በመሰቃየት ላይ ነህ፡፡ እና በጣም አዝናለሁ፡፡ እንዲህ በመሆኔ በጣም አዝናለሁ፡፡»
«በማዘን የትም አይደረስም፡፡»
አውቃለሁ የኔ ቆንጆ:: ግን ማዘን አይቀርም፡፡»
ዝም ዝም ሆነ
«በኔ ብቻ ሳይሆን በባህራምም ጭምር ነው ያዘንከው። ልክ
ዝም አልኳት
«እንግዲህ ልንገርህ፡፡ እውነቱን ብታውቅ ይሻላል። ልንገርህ?»
«እሺ፡፡»
«ያን እለት ማታ ያ ሰውዬ ባህራምን ሊገድለው አልመጣም?
እና አንተ ኒኮልን ይዘህ ማርዕይ አልሄድክም? ከኒኮል ጋር
ምንም አልሰራችሁም? እውነት ተናገር፡፡»
«ምንም አልሰራንም፡፡ ይልቅ ቀጥዪ።»
«እና ሰውየውን ሲገድለው አላየሁም? እሱን ነግሬሀለሁ። እና
ከዚያ ወደ ቤት ሄድን፡፡ ባህራም ልክ ምንም እንዳልስራ በእርጋታ
ሶፋ ላይ ተቀመጠ። እኔ መጠጥ ሰጠሁትና ሶፋው ላይ አልጋ ብጤ
አነጠፍኩለት፡፡ አንጥፌ ስጨርስ 'እንግዲህ እዚህ ውስጥ ይተኛል።
ነብስ ገድሏል፤ ግን እዚህ ውስጥ ይተኛል። ከጀግና ጋር ነው'ኮ
ያለሁት። ከነብሰ ገዳይ ጋር ነው ያለሁት ብዬ አሰብኩ፡፡ ዘወር ብዬ
አየሁት። አንተ እንደ ነገርከኝ ነው። ዝም ሲል የኢራንን ሻህ
ይመስላል። ግን ማን ያውቃል? ጀግና ስለሆነ አንድ ቀን የኢራንን
ሻህ ይገድለው ይሆናል'ኮ!' ብዬ አሰብኩ
«እና በሀይል ተመኘሁት፡፡ ፍትወት ያንን ያህል አንቆ ይዞኝ
አያውቅም፡፡ ራሴን 'ተይ እንደሱ አታርጊ! - ተይ!'
እያልኩ
ከተቀመጠበት ሄድኩና እግሩ አጠገብ ተምበርክኬ ወደላይ አየሁት።
እንደ ቄስ እጁን ራሴ ላይ አሳረፈና
«ምን ሆነሻል?» አለኝ
ቀስ ብዬ ተነሳሁና አፉ ላይ ሳምኩት
አሁንም «ምን ሆነሻል?» አለኝ። ግን ገብቶታል
«ፈልጌሀለሁ» አልኩት
«እኔ አልፈልግሽም» አለ
«አውቃለሁ ትፈልገኛለህ፡፡ ትፈልገኝ የለ?»
«አዎን፡፡ ካየሁሽ ጀምሮ እንደፈለግኩሽ ነው::»
«ይኸዋ፡፡ አለሁልህ!»
«አይሆንም!»
«ለምን አይሆንም?»
«ምክንያቱን መቼ አጣሽው» አንተን ማለቱ ነው
«እሱ ንደሆነ ግድ የለውም» ኣልኩት
«እኔ ግድ አለኝ!»
«ለምን?»
«ጓደኛዬ ነው:: እፈልግሻለሁ፡፡ ግን እሺ አልልሽም። ስለዚህ
እርሺው!»
«አልረሳውም፡፡ ልረሳው አልችልም፡፡ ልረሳው አልፈልግም።
ሌሊት እመጣለሁ!» አልኩትና ሄጄ አልጋዬ ውስጥ ገባሁ፡፡ ልተወው
ቆረጥኩ። ምናልባት አንድ ሰአት ያህል ቆየሁ። ከዚያ በላይ ግን
ልቆይ አልቻልኩም፡፡ እንደዚህ አላስችል ያለኝ እሱ ስለሆነ ብቻ
ነበር፣ ወይስ ሰው ሲገድል ስላየሁት ነበር? አላውቅም፡፡ የሆነ ሆኖ፣ እሱ እዚያ ተጋድሞ እኔ እዚህ ሆኜ ልታገስ አልቻልኩም
ራቁቴን ወጣሁ፡፡ ሽቶ ተቀባሁ፡፡ ከመኝታዬ ወጣሁ፡፡ የንግዳ
ቤቱን መብራት አበራሁ። እንቅልፍ አልወሰደውም ነበር። በቀጥታ
ሄድኩና ከበላዩ ቆምኩ፡፡ ወደላይ አየኝ፡፡ ሲያየኝ ብዙ ጊዜ ቆየ፡፡
እጁን ሰደደ። ጭኔን ይዞ ወደታች ጎተተኝ
ካሸነፈኩት በኋላ ወደ አልጋዬ ሄድን፡፡»
ዝም አለች፡፡ ያችን ሌሊት እንደምታስታውስ ያስታውቃል፡፡
እንዴት ያለች ሌሊት ነበረች ይሆን? ብጠይቃት እንደማትነግረኝ
እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ስለሌሎቹ ወንዶች በሰፊው ትንገረኝ እንጂ፣
ስለነሱ ጥቃቅኑን ስጋዊ ተግባር ሳይቀር ትዘርዝርልኝ እንጂ፣
ስለፖልና ስለ ባሀራም አትነግረኝም፡፡ እኔም ስለነሱ መጠየቅ ልክ አልመሰለኝም፡፡ ዝም አልኩ። ቀጠለች
«ስለሌሊቱ ልንገርህ እንዴ?» አለችኝ
«ልትነግሪኝ ትፈልጊያለሽ?»
«አልፈልግም። ከፈለግክ ግን እነግርሀለሁ።»
ይህን ያለችኝ «ሳትፈልጊ ብትነግሪኝ ደስ አይለኝም»
እንደምላት አውቃ ነው እንጂ፡ ንገሪኝ ብላትም እንደማትነግረኝ
አውቃለሁ
«ሳትፈልጊ ብትነግሪኝ ደስ አይለኝም» አልኳት
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አሮጌው ቤት
ከአርባ ዓመት በፊት እጅግ ጭር ያለ ሰፈር የነበረው ዛሬ ብዙ
ሕዝብ ይተራመስበታል፡፡ ገጠር መሆኑ ቀርቶ ወደ ከተማነት ተለውጧል፡፡ አካባቢው ዣን ቫልዣ ሲያውቀው ከፓሪስ ከተማ ወጣ ያለ ባላገር ነበር፡፡ዛሬ የከተማው አካል ሆኖአል፡፡ ብዙ ቤቶች ተሠርተዋል፤ መንገድም
ወጥቶለታል፡፡ ቢሆንም ግን የገጠርነት ስሜት አሁንም ይታይበታል፡፡ከመንገዱ ግራና ቀኝ ሳር በቅሎአል:: ቤቶቹም ቢሆኑ እስከዚህም የጸዱ አይደሉም፡፡ የፈረስ ገበያ ከዚያ አካባቢ ስለነበር የስፍራው ጽዳት ይህን
ያህል አያስደስትም::
ከዋናው መንገድ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚታይ ባለአንድ ፎቅ አሮጌ ቤት
አለ፡፡ በሮቹ በምስጥ ስለተበሉ አልፎ አልፎ ቀዳዳ ይታይባቸዋል:: የቤቱ መስኮቶች በጣም ሰፋፊ ናቸው:: የመስኮቶቹ መስታወት አንዳንዶቹ ስለተሰበሩ
በካርቶን መሳይ ወረቀቶች ተሸፍነዋል :: መጋረጃዎቹም ቢሆነ
ከመበለዛቸውም በላይ ጫፍ ጫፋቸው ተቀዳደዋል:: ወደ ፎቅ በሚያስወጣው መሰላል ሲራመዱ ደረጃው እንደ መዚቃ መሣሪያ ያፍጮሃል:: በረት የመሰለ
ትልቅ ክፍል ከሩቁ ይታያል፡፡ የዚህ ክፍል ሀለቱም መስኮቶች ሰፋፊ ሲሆኑ በዚያ በኩል ወደ ውጭ በማየት በመንገድ የሚያልፈውን ማየት ይቻላል::የቤቱ ቁጥሩ 5052 ነው
ዣን ቫልዣ ከዚህ አሮጌ ቤት አጠገብ ሲደርስ ቆም ብሎ ቤቱን
አየው:: ጭልፊት የሚያሳድዳት ጫጩት የተሰወረ ከለላ እንደምትፈልግ ሁሉ እርሱም ከነዣቬር ለመሰወር ከለላ ይፈልጋል:: የዚህ ቤት አቀማመጥ
ደግሞ በጣም የተሰወረ ስለነበር የሚፈልገውን ያገኘ መሰለው፡፡ ከኪሱ ውስጥ ቁልፍ አውጥቶ በሩን ከፈተው:: ከገባ በኋላ መልሶ ዘጋው:: ኮዜትን ታቅፎ በደረጃው ወደ ፎቅ ወጣ፡፡ ደረጃውን ወጥቶ ሲጨርስ ሌላ ቁልፍ ከኪሱ አወጣ፡፡ የተቆለፈውን በር ከፍቶ ወደ አንድ ክፍል ገባ፡፡
ስፋ ካለ ክፍል ወለል ላይ ትልቅ ፍራሽ ተዘርግቷል፡፡ ጥቂት
ቦታ ወንበሮችና ጠረጴዛም አለ፡፡ የእሳት ማንደጃ ከአንድ ጥግ ይታያል:: አንድ ትንሽ የልጅ አልጋም አለ፡፡ ዣን ቫልዣ ቀስ ብሎ ኮዜት ሳትነቃ ከትንሹ አልጋ ላይ አስተኛት::
በሩን መልሶ ከዘጋ በኋላ ሻማ አበራ:: የመንገዱ መብራት ክፍሉን
ያሳይ ስለነበር ሻማ እስካበራ ድረስ በጨለማ አልተንገዳገደም:: በአለፈው ቀን እንዳደረገው ሁሉ ኮዜት ተኝታ ሳለ ዐይኑን ከዐይንዋ አላነሳም:: ለረጅም ጊዜ ኣፍጥጦ ተመለከታት:: ኮዜት ከማን ጋርና የት እንደተኛች ሳታውቅ ለብዙ ሰዓት እንቅልፍዋን ለጠጠች::
ዣን ቫልዣ ጎንበስ ብሎ እጅዋን ሳማት:: ከዘጠኝ ወር በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ እንቅልፍ ወስዶአት ሳለ የእናትዋን እጅ ስሞ ነበር፡፡
ተመሳሳይ የሆነ የሀዘኔታና የጭንቀት ስሜት ተሰማው:: ኮዜት ከተኛችበት አልጋ አጠገብ ተንበረከከ፡፡
ወገግ ብሎ ነግቷል:: ግን ልጅትዋ አሁንም እንቅልፍ እንደወሰዳት
ናት። ከባድ እቃ የጫነ ጋሪ በዚያ ሲያልፍ ያንን አሮጌ ፎቅ ቤት አነቃነቀው፡፡ ኳኳታው በኃይል ስለነበር እንኳን የትኛን የሞተን ይቀሰቅሳል ማለቱ የድምፁን ብርታት መግለጽ እንጂ ማጋነን አይሆንም::
«እመት እመቤቴ» አለች ኮዜት ፈንጠር ብላ ከአልጋው እየተነሳች::
ቀጠለችና ደግሞ መጣሁ መጣሁ» ስትል ጮኸች:: ዓይንዋን ሳትገልጥ ካልጋው ዘላ ወረደች።
እየተንጠራራች ወደ ግድግዳው ሄደች።
«ወይ ጣጣ፤ መጥረጊያው የት አለ!» አለች::
ኣሁን ዓይንዋን ገልጣለች:: በፈገግታ ያጌጠ የዣን ቫልዣን ፊት
ተመለከተች::
«እህ! ለካስ…» አለች ልጅትዋ ፧ «እንደምን አደሩ ጌታዬ::»
ቶሉ ብሎ አካባቢውን መላመድና ባለው መደሰት የልጆች ባህርይ
ነው:: ተደሳች ሁነው ሰው ያስደስታሉ፡፡
ኮዜት ካተሪንን ከአልጋዋ ስር አየቻት፡፡ ወዲያው ብድግ አድርጋ
አቀፈቻት፡፡ ከአሻንጉሊቱ ጋር እየተጫወተች ዣን ቫልዣን የመዓት ጥያቄ ጠየቀችው:: የት ነበረች? ፓሪስ ትልቅ ከተማ ነው? አሁን መዳም ቴናድዬ ከዚህ አይመጡም? ከዚህ የሚስስ ቴናድዬ ቤት ምን ያህል ይርቃል?
ሌላም፧ ሌላም፡፡ በመስኮቱ ወደ ውጭ አይታ «እንዴት ያምራል፤ እንዴት ደስ ይላል» ስትል ተናገረች::
የነበረችበት ሁኔታ በመጠኑም ቢሆን ያስፈራ ነበር፡፡ ነገር ግን
እርስዋ ነፃ የወጣች መሰላት::
«ቤቱን ልጥረግ?» ስትል ጠየቀች::
«የለም፧ ተጫወች» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰላት::
ስትጫወት ቀኑ አለፈ:: ስላለችበት ሥፍራም ሆነ ሁኔታ ለማወቅ
ራስዋን ሳታስጨንቅ ከአሻንጉሊትዋ ጋርና ከጓደኛዋ ጋር እየተጫወተች ደስ ብሎአት ነበር የዋለችው::
በሚቀጥለው ቀን ጎሕ ሲቀድ እንዳለፈው ቀን ኮዜት ስትነቃ ለማየት ዣን ቫልዣ ከአልጋው አጠገብ ሲቀመጥ አዲስ ስሜት ተሰማው፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ በፊት ምንም ነገር አፍቅሮ አያውቅም፡፡ ትዳር ሳይዝ፣ ልጅ ሳይወልድ ፤ ሴት ሳያፈቅርና የልብ ጓደኛ ሳያበጅ ለሃያ አምስት ዓመት ብቻውን ነው የኖረው:: እስር ቤት ሆኖ ኑሮው የጨለማና የስቃይ ነበር፡፡
ዣን ቫልዣ እስር ቤት ከመግባቱ አስቀድሞ ከቤቱ ሲወጣ ልቡ በተስፋ የደነደነ፤ ሐሞተ ሙሉ ሰው ነበር:: እህቱና ልጆችዋ ከሕሊናው ጨርሰው
ባይፋቱም በአሳብ የሚታዩት እጅግ ተንነው ሲሆን እነርሱን ለማግኘት ብዙ ጥረት አደረገ፡፡ ግን አላገኛቸውም:: ጊዜ እንደሚሽረው እንደማንኛውም ነገር ከጊዜ በኋላ ግን ረሳቸው:: ሌሎችም በወጣትነት ዘመኑ የሚያውቃቸው
ነገሮች ሁሉ እንደዚሁ ከሕሊናው ውስጥ መንምነው ጠፍተዋል፡፡
ኮዜትን አግኝቶ ከዚያ የስቃይና የመከራ ኑሮ ሲያወጣትና ይዞአት
ሲሄድ ስሜቱ እጅግ ይነካል፡፡ ይህም ለሰው ልጅ የነበረውን ፍቅር ቀሰቀሰበት። የፍቅሩ ጽናት ከዚህች ልጅ ዙሪያ ተሰባሰበ፡፡ ወደ ኮዜት አልጋ ጠጋ ብሎ ሲመለከታት ልቡ በደስታ ፈካ:: እናት ለልጅዋ ፍቅር እንደምትብረከረክ ሁሉ እሱም በዚህች ልጅ ፍቅር መዋጡ ገረመው፡፡
የፍቅሩ ግለትና የሀዘኔታው ብዛት ሊገባውና በቃላት ሊገልጸው ከሚችለው እርሱ ሃምሣ አምስት ዓመቱ ሲሆን እርስዋ ስምንት ዓመትዋ ነው:: ስለዚህ ፍቅሩ ግሪኮች አጋፔ ብለው የሚጠሩት እናት ለልጅዋ ያላት ፍቅር
ዓይነት እንጂ የሌላ አልነበረም፡፡
በሕይወት ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ የሕይወት ተመስጦአዊና አስጨናቂ ትርኢት አየ፡፡ ከእስር ቤት ሲወጣ ያገኛቸው ጳጳስ የሕይወቱን አድማስ
ያሰፉለትና የሕይወት ጣዕም ሕያቀደዱለት የመጀመሪያው ፍጡር ናቸው፡፡
ኮዚት ደግሞ ተጨማሪ የፍቅር ጎሕ ከፈተችለት፡፡ ይህንኑ እያሰላሰለ ጥቂት ቀናት አለፉ::
አሳዛኝዋና ምስኪንዋ ኮዜትም ቢሆን ሳይታወቃት እየተለወጠች
ነበረ፡፡ እናትዋ ጥላት ስትሄድ ጨቅላ ልጅ ነበረች፡፡ በዚያን ጊዜ ምን ትመስል እንደነበር ለማስታወስ አትችልም፡፡ ልጆች እንደ ሐረግ ካገኙት ላይ እንደሚጠመጠሙ ሁሉ እርስዋም ከሰዎች ላይ ተጠምጥማ ለማፍቀር ብትሞክርም ሰዎች የማፍቀር እድል አልሰጥዋትም ነበር፡፡ እነሚስተር ቴናድዬ ፤ ልጆቻቸውና ሌሉችም ቢሆኑ ፍቅር አላሳይዋትም: ከቤታቸው
የነበረውን ውሻ ትወደው ነበር፡፡ ግን እሱም ሞተ፡፡ ውሻው ከሞተ ጀምሮ እንኳን ሰው የቤት እንሰሳም ቢሆን አላቀረባትም:: ስለዚህ ጥፋቱ የእርስዋ ባይሆንም ገና በስምንት ዓመትዋ ለሰው ፍቅር አልነበራትም:: ቢወድዋት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
አሮጌው ቤት
ከአርባ ዓመት በፊት እጅግ ጭር ያለ ሰፈር የነበረው ዛሬ ብዙ
ሕዝብ ይተራመስበታል፡፡ ገጠር መሆኑ ቀርቶ ወደ ከተማነት ተለውጧል፡፡ አካባቢው ዣን ቫልዣ ሲያውቀው ከፓሪስ ከተማ ወጣ ያለ ባላገር ነበር፡፡ዛሬ የከተማው አካል ሆኖአል፡፡ ብዙ ቤቶች ተሠርተዋል፤ መንገድም
ወጥቶለታል፡፡ ቢሆንም ግን የገጠርነት ስሜት አሁንም ይታይበታል፡፡ከመንገዱ ግራና ቀኝ ሳር በቅሎአል:: ቤቶቹም ቢሆኑ እስከዚህም የጸዱ አይደሉም፡፡ የፈረስ ገበያ ከዚያ አካባቢ ስለነበር የስፍራው ጽዳት ይህን
ያህል አያስደስትም::
ከዋናው መንገድ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚታይ ባለአንድ ፎቅ አሮጌ ቤት
አለ፡፡ በሮቹ በምስጥ ስለተበሉ አልፎ አልፎ ቀዳዳ ይታይባቸዋል:: የቤቱ መስኮቶች በጣም ሰፋፊ ናቸው:: የመስኮቶቹ መስታወት አንዳንዶቹ ስለተሰበሩ
በካርቶን መሳይ ወረቀቶች ተሸፍነዋል :: መጋረጃዎቹም ቢሆነ
ከመበለዛቸውም በላይ ጫፍ ጫፋቸው ተቀዳደዋል:: ወደ ፎቅ በሚያስወጣው መሰላል ሲራመዱ ደረጃው እንደ መዚቃ መሣሪያ ያፍጮሃል:: በረት የመሰለ
ትልቅ ክፍል ከሩቁ ይታያል፡፡ የዚህ ክፍል ሀለቱም መስኮቶች ሰፋፊ ሲሆኑ በዚያ በኩል ወደ ውጭ በማየት በመንገድ የሚያልፈውን ማየት ይቻላል::የቤቱ ቁጥሩ 5052 ነው
ዣን ቫልዣ ከዚህ አሮጌ ቤት አጠገብ ሲደርስ ቆም ብሎ ቤቱን
አየው:: ጭልፊት የሚያሳድዳት ጫጩት የተሰወረ ከለላ እንደምትፈልግ ሁሉ እርሱም ከነዣቬር ለመሰወር ከለላ ይፈልጋል:: የዚህ ቤት አቀማመጥ
ደግሞ በጣም የተሰወረ ስለነበር የሚፈልገውን ያገኘ መሰለው፡፡ ከኪሱ ውስጥ ቁልፍ አውጥቶ በሩን ከፈተው:: ከገባ በኋላ መልሶ ዘጋው:: ኮዜትን ታቅፎ በደረጃው ወደ ፎቅ ወጣ፡፡ ደረጃውን ወጥቶ ሲጨርስ ሌላ ቁልፍ ከኪሱ አወጣ፡፡ የተቆለፈውን በር ከፍቶ ወደ አንድ ክፍል ገባ፡፡
ስፋ ካለ ክፍል ወለል ላይ ትልቅ ፍራሽ ተዘርግቷል፡፡ ጥቂት
ቦታ ወንበሮችና ጠረጴዛም አለ፡፡ የእሳት ማንደጃ ከአንድ ጥግ ይታያል:: አንድ ትንሽ የልጅ አልጋም አለ፡፡ ዣን ቫልዣ ቀስ ብሎ ኮዜት ሳትነቃ ከትንሹ አልጋ ላይ አስተኛት::
በሩን መልሶ ከዘጋ በኋላ ሻማ አበራ:: የመንገዱ መብራት ክፍሉን
ያሳይ ስለነበር ሻማ እስካበራ ድረስ በጨለማ አልተንገዳገደም:: በአለፈው ቀን እንዳደረገው ሁሉ ኮዜት ተኝታ ሳለ ዐይኑን ከዐይንዋ አላነሳም:: ለረጅም ጊዜ ኣፍጥጦ ተመለከታት:: ኮዜት ከማን ጋርና የት እንደተኛች ሳታውቅ ለብዙ ሰዓት እንቅልፍዋን ለጠጠች::
ዣን ቫልዣ ጎንበስ ብሎ እጅዋን ሳማት:: ከዘጠኝ ወር በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ እንቅልፍ ወስዶአት ሳለ የእናትዋን እጅ ስሞ ነበር፡፡
ተመሳሳይ የሆነ የሀዘኔታና የጭንቀት ስሜት ተሰማው:: ኮዜት ከተኛችበት አልጋ አጠገብ ተንበረከከ፡፡
ወገግ ብሎ ነግቷል:: ግን ልጅትዋ አሁንም እንቅልፍ እንደወሰዳት
ናት። ከባድ እቃ የጫነ ጋሪ በዚያ ሲያልፍ ያንን አሮጌ ፎቅ ቤት አነቃነቀው፡፡ ኳኳታው በኃይል ስለነበር እንኳን የትኛን የሞተን ይቀሰቅሳል ማለቱ የድምፁን ብርታት መግለጽ እንጂ ማጋነን አይሆንም::
«እመት እመቤቴ» አለች ኮዜት ፈንጠር ብላ ከአልጋው እየተነሳች::
ቀጠለችና ደግሞ መጣሁ መጣሁ» ስትል ጮኸች:: ዓይንዋን ሳትገልጥ ካልጋው ዘላ ወረደች።
እየተንጠራራች ወደ ግድግዳው ሄደች።
«ወይ ጣጣ፤ መጥረጊያው የት አለ!» አለች::
ኣሁን ዓይንዋን ገልጣለች:: በፈገግታ ያጌጠ የዣን ቫልዣን ፊት
ተመለከተች::
«እህ! ለካስ…» አለች ልጅትዋ ፧ «እንደምን አደሩ ጌታዬ::»
ቶሉ ብሎ አካባቢውን መላመድና ባለው መደሰት የልጆች ባህርይ
ነው:: ተደሳች ሁነው ሰው ያስደስታሉ፡፡
ኮዜት ካተሪንን ከአልጋዋ ስር አየቻት፡፡ ወዲያው ብድግ አድርጋ
አቀፈቻት፡፡ ከአሻንጉሊቱ ጋር እየተጫወተች ዣን ቫልዣን የመዓት ጥያቄ ጠየቀችው:: የት ነበረች? ፓሪስ ትልቅ ከተማ ነው? አሁን መዳም ቴናድዬ ከዚህ አይመጡም? ከዚህ የሚስስ ቴናድዬ ቤት ምን ያህል ይርቃል?
ሌላም፧ ሌላም፡፡ በመስኮቱ ወደ ውጭ አይታ «እንዴት ያምራል፤ እንዴት ደስ ይላል» ስትል ተናገረች::
የነበረችበት ሁኔታ በመጠኑም ቢሆን ያስፈራ ነበር፡፡ ነገር ግን
እርስዋ ነፃ የወጣች መሰላት::
«ቤቱን ልጥረግ?» ስትል ጠየቀች::
«የለም፧ ተጫወች» ሲል ዣን ቫልዣ መለሰላት::
ስትጫወት ቀኑ አለፈ:: ስላለችበት ሥፍራም ሆነ ሁኔታ ለማወቅ
ራስዋን ሳታስጨንቅ ከአሻንጉሊትዋ ጋርና ከጓደኛዋ ጋር እየተጫወተች ደስ ብሎአት ነበር የዋለችው::
በሚቀጥለው ቀን ጎሕ ሲቀድ እንዳለፈው ቀን ኮዜት ስትነቃ ለማየት ዣን ቫልዣ ከአልጋው አጠገብ ሲቀመጥ አዲስ ስሜት ተሰማው፡፡ ዣን ቫልዣ ከዚያ በፊት ምንም ነገር አፍቅሮ አያውቅም፡፡ ትዳር ሳይዝ፣ ልጅ ሳይወልድ ፤ ሴት ሳያፈቅርና የልብ ጓደኛ ሳያበጅ ለሃያ አምስት ዓመት ብቻውን ነው የኖረው:: እስር ቤት ሆኖ ኑሮው የጨለማና የስቃይ ነበር፡፡
ዣን ቫልዣ እስር ቤት ከመግባቱ አስቀድሞ ከቤቱ ሲወጣ ልቡ በተስፋ የደነደነ፤ ሐሞተ ሙሉ ሰው ነበር:: እህቱና ልጆችዋ ከሕሊናው ጨርሰው
ባይፋቱም በአሳብ የሚታዩት እጅግ ተንነው ሲሆን እነርሱን ለማግኘት ብዙ ጥረት አደረገ፡፡ ግን አላገኛቸውም:: ጊዜ እንደሚሽረው እንደማንኛውም ነገር ከጊዜ በኋላ ግን ረሳቸው:: ሌሎችም በወጣትነት ዘመኑ የሚያውቃቸው
ነገሮች ሁሉ እንደዚሁ ከሕሊናው ውስጥ መንምነው ጠፍተዋል፡፡
ኮዜትን አግኝቶ ከዚያ የስቃይና የመከራ ኑሮ ሲያወጣትና ይዞአት
ሲሄድ ስሜቱ እጅግ ይነካል፡፡ ይህም ለሰው ልጅ የነበረውን ፍቅር ቀሰቀሰበት። የፍቅሩ ጽናት ከዚህች ልጅ ዙሪያ ተሰባሰበ፡፡ ወደ ኮዜት አልጋ ጠጋ ብሎ ሲመለከታት ልቡ በደስታ ፈካ:: እናት ለልጅዋ ፍቅር እንደምትብረከረክ ሁሉ እሱም በዚህች ልጅ ፍቅር መዋጡ ገረመው፡፡
የፍቅሩ ግለትና የሀዘኔታው ብዛት ሊገባውና በቃላት ሊገልጸው ከሚችለው እርሱ ሃምሣ አምስት ዓመቱ ሲሆን እርስዋ ስምንት ዓመትዋ ነው:: ስለዚህ ፍቅሩ ግሪኮች አጋፔ ብለው የሚጠሩት እናት ለልጅዋ ያላት ፍቅር
ዓይነት እንጂ የሌላ አልነበረም፡፡
በሕይወት ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ የሕይወት ተመስጦአዊና አስጨናቂ ትርኢት አየ፡፡ ከእስር ቤት ሲወጣ ያገኛቸው ጳጳስ የሕይወቱን አድማስ
ያሰፉለትና የሕይወት ጣዕም ሕያቀደዱለት የመጀመሪያው ፍጡር ናቸው፡፡
ኮዚት ደግሞ ተጨማሪ የፍቅር ጎሕ ከፈተችለት፡፡ ይህንኑ እያሰላሰለ ጥቂት ቀናት አለፉ::
አሳዛኝዋና ምስኪንዋ ኮዜትም ቢሆን ሳይታወቃት እየተለወጠች
ነበረ፡፡ እናትዋ ጥላት ስትሄድ ጨቅላ ልጅ ነበረች፡፡ በዚያን ጊዜ ምን ትመስል እንደነበር ለማስታወስ አትችልም፡፡ ልጆች እንደ ሐረግ ካገኙት ላይ እንደሚጠመጠሙ ሁሉ እርስዋም ከሰዎች ላይ ተጠምጥማ ለማፍቀር ብትሞክርም ሰዎች የማፍቀር እድል አልሰጥዋትም ነበር፡፡ እነሚስተር ቴናድዬ ፤ ልጆቻቸውና ሌሉችም ቢሆኑ ፍቅር አላሳይዋትም: ከቤታቸው
የነበረውን ውሻ ትወደው ነበር፡፡ ግን እሱም ሞተ፡፡ ውሻው ከሞተ ጀምሮ እንኳን ሰው የቤት እንሰሳም ቢሆን አላቀረባትም:: ስለዚህ ጥፋቱ የእርስዋ ባይሆንም ገና በስምንት ዓመትዋ ለሰው ፍቅር አልነበራትም:: ቢወድዋት
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...መቼም ባልቻን በግልፍተኛነት የሚያማዉ አይገኝም የጃሪምን ግልምጫ ከምንም ሳይቆጥር ፈገግ ብሎ አሳለፈዉና፣ ወደኔ መጥቶ አቀፈኝ፡ እሱን
እዚህ መሆኔን እንዴት አወቀ አይሉትም፡ እኔም በችኮላ ተንከረፈፍሁ እንጂ የትም ብሄድ ከሲራክ ፯ ማምለጥ እንደማልችል ማስተዋል ነበረብኝ፡ እንኳንስ እንደዚህ ተንዘላዝዬለት ይቅርና! የንዝህላልነቱ ንዝህላልነት ደግሞ በገዛ ስልኬ ለሸዊት ስልክ መደወሌ፡ በዚህ ስሕተቴ
እንኳንስ የሲራክ ፯ቱ ባልቻ፣ የተናቀ የመንደር ደመኛ እንኳን ሊያገኘኝ ይችላል።
ባልቻ ከመግባቱ አፍታ ሳይቆዩ እሸቴ እና ሸዊት ተከታትለዉ ገቡ።
“አንቺ?” ስል ተቀበልኋት፣ ከእሸቴ ኋላ መጥታ ለሰላምታ ስታቅፈኝ፡
“እንዲያዉ እስካሁን እያለቀሰችም ቢሆን ገና አሁን ነው የምትደርሽልኝ ማለት ነዉ?” አልኋት፣ ለቂሜ መወጫ ጠበቅ አድርጌ እያቀፍኋት።
የአሁኑ መተቃቀፋችን ትርጉሙ የትየለሌ ነዉ: አንድም በሆስፒታል
ቆይታዬ ዓይንሽን ለአፈር ብያት የነበረዉን ኩርፊያ ጨርሼ ረሳሁላት፣አንድም ለቱናት አምጭልኝ ያልኋትን ወተት ያዉም የሚሆናትን መጠጫ ጡጦ ጭምር ስላመጣችልኝ አመሰገንኋት፣ አንድም ነባሩ
ሰላምታችን እንደዚህ ነዉ፡ እንደገና እቅፍ አድርጌ ጨመቅኋት።
"እ?"
“ኧረ እኔስ ወዲያዉ ነበር የደረስሁት”
“አዎ” አለ ባልቻ፣ ክንዱን ትከሻዋ ላይ እየጫነ፡ “ወተቱን ብቻ ይዛ
ስትመጣ አግኝቻት፣ እኔ ነኝ ጡጦም ጨምራችሁ አምጡ ብዬ ከእሸቴ ጋ መልሼ የላክኋቸዉ። መቼም ምን ዶክተር ብትሆን፣ በዕድሜ ታናሼ ስለሆነች፣ በዚህ ቅር የምትሰኝብኝ አይመስለኝም”
“ኧረ በጭራሽ!” አለች፣ ወተቱን እና የጡጦ እቃዉን እያቀበለችኝ:
“ኧረ ስሚኝማ ዉቤ” አለች፣ የመደነቅ ፊቷን እየገለጠችልኝ፡፡
“ምን”
“ወንድምሽን እኮ ሊፍቱ ጋ አግኝቼዉ አሁን''
“ማንን?” አልኋት ለወጉ፣ ማንን ማለቷ እንደሆነ ባላጣዉም፡፡
“ጀሪምን ነዋ”
“እሺ”
“ምን እሺ ትይኛለሽ? ሰላምታ ከልክሎኝ ሄደ እኮ”
“ኧረ?” አልኋት፣ ከእሽጉ ዉሃ ከፍቼ ወደ ጡጦዋ እየቀነስሁ ዉሃዉ መቼ እንደ ተቀመጠልኝ ግን አላወቅሁም: ከአጠገቡ ሶፍት፣ ፎጣ እና ሌሎች አልባሌ ነገሮችም መኖራቸዉን ሳይ ማረፊያ ክፍሉን ከመያዜ
በፊትም ተቀምጠዉ እንደነበር ገባኝ፡፡
“አይገርምሽም? መቼስ ረስቶሽ ነዉ አትዪኝም ጃሪም እኔን ሊረሳ? ጉድ እኮ ነዉ! ያኔ እንዲያ …” ብላ፣ ተገርማ ቀረች፡፡ እየቆየ እንደገና በኃይል ከነከናት፡ ምክንያቷን አላጣሁትም፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሳለን ለአንድ ዕረፍት እኛ ቤት በነበርንበት ጊዜ፣ ጃሪም ዓይን አብዝቶባት ነበር
እንዲያዉም ደጋግሞ ወድጃታለሁ እንዳለኝ አስታዉሳለሁ ስሜቱን በግልጽ ለእሷ እንደ ነገራት ግን አላውቅም፡ ከአሁኑ ሁኔታዋ
እንዳስተዋልሁት ከሆነ፣ መንገር ብቻም ሳይሆን እሞትልሻለሁ› ጭምር ሳይላት እንዳልቀረ ገመትሁ ያ ሁሉ ቀርቶ አሁን ግን እንደማያዉቃት ከሆነባት፣ ባይገርማት ነበር የሚገርመኝ፡ ያዉ፣ የእኔ ጓደኛ አይደለች?
በእሱ ቤት እኮ አሁን፣ የእኔ የሆነ እና እኔ የነካሁት ሁሉ ርኩስ
ሆኖበታል።
“አጀብ ነዉ አለ ጅብ? የሆነዉስ ይሁንና በምን ዝም አሰኘሻት?” አለች፣ ቱናትን ገለጥ እያደረገቻት፡ ከጀርባዋ አጥንት ላይ ላለዉ ቁስል ጥንቃቄ አድርጋላት፣ አቀፈቻት እና ልትቀመጥ ብትፈልግ መቀመጫ አጣች: ገና
ይኸኔ ነዉ የሆቴል ማረፊያ ክፍል ዉስጥ መሆኔ ራሱ ትዝ ያላት:
የጃሪምን ፊት መንሳት ማመን አቅቷት ዋናዉን ጥያቄዋን እንደ ረሳችዉ ልብ አደረገች፡፡
“ቆይ ቆይ፣ አንቺ ግን እዚህ ምን ትሠሪያለሽ? ከእመዋ ቤት ያዉም ያን ድግስ ጥለሽ? ያዉም ይቺን ጨቅላ ይዘሽ? ምን ልትሆኚ እዚህ መጣሽ በይ?”
ይኸዋ! እንደ ፈራሁት የማርያም መንገድ እንኳን ሳታስቀርልኝ ጥያቄዋን አመጣችዉ ያልሰማሁ መስዬ ዝም ልላት ፈልጌ ነበር፡ ነገር ግን እሷን ሽሽት ዓይኔን የጣልሁበት ባልቻም ከእሷ በላይ አፈጠጠብኝ፡፡ ለራሱ ጉዳይ
ቢሆን፣ ሽንቱ እንኳን የፈለገ ወጥሮ ቢይዘዉ የሲራክ ፯ ጉዳይ ፋታ
እንደማይሰጠዉ እያወቅሁ፣ ለእኔ ሲል ነዉ አትረፍርፎ የሚሰጠኝ። እኔ ግን እንደ ደመኛ ተደብቄዉ እዚህ ሲያገኘኝ ማዘን ይበቃዉ ይሆን? እንኳን ማኩረፍ ሌላም ቢያደርግ እዉነት አለዉ፡ ግን እሱ ነዉና ሰዉዬዉ፣ መተዉ ያዉቅበታል፡ ያም ቢሆን ግን ጥያቄዋን ተጋርቷታል።
እንድመልስላት ከእሷ እኩል እየተቁለጨለጨብኝ ሳለ እሸቴ በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ መቼ እንደ ወጣ ግን አላየሁትም ነበር፡፡ ለካንስ እመዋ ደዉላለት፣ እሷን ለማነጋገር ወጥቶ ኖሯል።
“እመዋ ናት የደወለችልኝ። (ልምጣ ወይ እያለች ነዉ፣ ትምጣ እንዴ?" አለ፣ ሳይታወቀዉ በሸዊትና
በባልቻ ከተፋጠጥሁበት ጥያቄ
ሲያስመልጠኝ፡ ባልቻ ቅር እንዳለዉም ቢሆን ቸለል አለልኝ፡ ሸዊትም እንዲሁ ቱናትን እንዳቀፈቻት ከአልጋዉ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ወተቱን ለማጥባት ሞከረች::
“እናንተ?” አለች፣ ወተቱን ልታጠጣት ሞክራ ሞክራ እንዳልሆነላት ስታዉቅ ተስፋ እየቆረጠች። “ቱናት የተለየ ልምምድ ሳያስፈልጋት
አይቀርም: ከተወለደች አንስቶ ኹለቱን ወር ሙሉ የከረመችዉ ግሉኮስ ተተክሎላት ስለነበር፣ ከጡትም ሆነ ከጡጦ ምግብ ስትሞክር ይኼ የመጀመሪያዋ ነዉ። ስለዚህ፣ እንደኔ እንደኔ አሁኑኑ ወደ ሆስፒታል ተመልሳ መግባት ያለባት ይመስለኛል” አለች፣ እኔ ደግሞ እንድሞክራት
እያቀበለችን፡ “ለጊዜዉ ጉሉኮሱም ቢሆን ማግኘት አለባት” አታዩትም
አተነፋፈሷንስ? የባሰ ሲር ሲር እያለ እኮ ነዉ። ለመሆኑ የቀጣይ
ሕክምናዋን ጉዳይ አማክራ ችሁበታል ወይ?”
“ማንን፣ ይኼዉ አንቺ አለሽል አይደል? አንቺዉ ምከሪን እጂ” አለ ባልቻ፣ እኔም እንደዚሁ ልላት ስል ቀድሞኝ፡፡
ይኼ ሙያዬ አይደለም: ስለዚህ እኔ በቅጡ ከምፈተፍት፣ ጉዳዩን ይሁነኝ ብለዉ የተማሩት
ባለሙያዎች ስላሉ ወደ እነሱ መሄድ ይኖርብናል”
«የት ናቸዉ እነሱ ታዲያ?”
“ምን እሱማ ባላውቃቸውስ በአብዛኛዉ ሆስፒታሎች አይጠፉም ነበር:: ግን የመሣሪያዎች ዉስንነት አለ: ለጊዜዉ ሕክምናዉ በኹለት
ሆስፒታሎች ብቻ እንደሚገኝ ነዉ የማዉቀዉ”
“በስመ አብ!” አለ ባልቻ፡ “ወረፋዉ አያድርስ ነዉ በይኛ''
“በጣም!”
ከመንግሥት ሆስፒታሎች መካከል ይኼን ሕመም ጉዳዬ ብሎ በብቸኝነት ሕክምና ወደሚሰጠዉ ዘዉዲቱ ሆስፒታል ሄድን፡፡ አቤት ወረፋዉ! ያሉት
አልጋዎች ዉስን ናቸዉ፤ ተመዝግቦ ተራዉን የሚጠባበቀዉ ግን የትየለሌ! እንዲያዉም የኋላ ኋላ እንደ ሰማነዉ ከሆነስ፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ብቻ ከሃያ ሺ የሚበልጡ ሕጻናት የቱናት ዓይነት እክል ያጋጥማቸዋል አሉ፡ ቁጥሩን አሰብሁት ስንት የሚወራላቸዉ
ወረርሽኞችም እኮ ከዚህ የከፉ አይደሉም
የቱናንት ሁኔታ አጣዳፊ መሆኑን ልናስረዳ ብንልም፣ የሚሰማን
አላገኘንም: አብዛኛዉ እዚህ የመጣዉ ሰዉ ሁሉ ቱናት ካለችበት የሚተናነስ አለመሆኑን አምነን ተቀበልን፡፡ ሆኖም ሕክምናዉን በተመለከተ እስከሚወሰንልን ድረስ፣ ባይሆን በረኀብ እንዳትሞትብን በሚል ግሉኮስ ተፈቅዶልን አንድ ጥግ ላይ ተተከለላት:: በረንዳ ላይ:
መኝታ ክፍልማ የሚታሰብም አይደለም፡
“በቃ እናንተ ሂዱ እጂ” አልኋቸዉ፣ ለግማሽ ሰዓት ያህል እንደዚሁ
እንደ ቆየን፡፡ እሳቱ የማይበርድ ችግር እየተጠባበቃቸዉ ሳለ፣ የሦስቱም እዚህ መቀመጥ ከቱናት ሕክምና ባልተናነሰ አሳስቦኛል ሸዊትም ፋታ የለሽ ሐኪም ናት፣ ባልቻም ባልቻ ነዉ፣ እሸቴም ያዉ ነዉ፡፡ “ሂዱ አረ! ሂዱ” አልሁኝ፣ እንደማግባባትም እንደማጣደፍም እያደረግሁ::
“መጨረሻዉን ሳንሰማ?” አለ ባልቻ፣ ስልክ ስልኩን ሲያይ እንዳልነበር ሁሉ፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
...መቼም ባልቻን በግልፍተኛነት የሚያማዉ አይገኝም የጃሪምን ግልምጫ ከምንም ሳይቆጥር ፈገግ ብሎ አሳለፈዉና፣ ወደኔ መጥቶ አቀፈኝ፡ እሱን
እዚህ መሆኔን እንዴት አወቀ አይሉትም፡ እኔም በችኮላ ተንከረፈፍሁ እንጂ የትም ብሄድ ከሲራክ ፯ ማምለጥ እንደማልችል ማስተዋል ነበረብኝ፡ እንኳንስ እንደዚህ ተንዘላዝዬለት ይቅርና! የንዝህላልነቱ ንዝህላልነት ደግሞ በገዛ ስልኬ ለሸዊት ስልክ መደወሌ፡ በዚህ ስሕተቴ
እንኳንስ የሲራክ ፯ቱ ባልቻ፣ የተናቀ የመንደር ደመኛ እንኳን ሊያገኘኝ ይችላል።
ባልቻ ከመግባቱ አፍታ ሳይቆዩ እሸቴ እና ሸዊት ተከታትለዉ ገቡ።
“አንቺ?” ስል ተቀበልኋት፣ ከእሸቴ ኋላ መጥታ ለሰላምታ ስታቅፈኝ፡
“እንዲያዉ እስካሁን እያለቀሰችም ቢሆን ገና አሁን ነው የምትደርሽልኝ ማለት ነዉ?” አልኋት፣ ለቂሜ መወጫ ጠበቅ አድርጌ እያቀፍኋት።
የአሁኑ መተቃቀፋችን ትርጉሙ የትየለሌ ነዉ: አንድም በሆስፒታል
ቆይታዬ ዓይንሽን ለአፈር ብያት የነበረዉን ኩርፊያ ጨርሼ ረሳሁላት፣አንድም ለቱናት አምጭልኝ ያልኋትን ወተት ያዉም የሚሆናትን መጠጫ ጡጦ ጭምር ስላመጣችልኝ አመሰገንኋት፣ አንድም ነባሩ
ሰላምታችን እንደዚህ ነዉ፡ እንደገና እቅፍ አድርጌ ጨመቅኋት።
"እ?"
“ኧረ እኔስ ወዲያዉ ነበር የደረስሁት”
“አዎ” አለ ባልቻ፣ ክንዱን ትከሻዋ ላይ እየጫነ፡ “ወተቱን ብቻ ይዛ
ስትመጣ አግኝቻት፣ እኔ ነኝ ጡጦም ጨምራችሁ አምጡ ብዬ ከእሸቴ ጋ መልሼ የላክኋቸዉ። መቼም ምን ዶክተር ብትሆን፣ በዕድሜ ታናሼ ስለሆነች፣ በዚህ ቅር የምትሰኝብኝ አይመስለኝም”
“ኧረ በጭራሽ!” አለች፣ ወተቱን እና የጡጦ እቃዉን እያቀበለችኝ:
“ኧረ ስሚኝማ ዉቤ” አለች፣ የመደነቅ ፊቷን እየገለጠችልኝ፡፡
“ምን”
“ወንድምሽን እኮ ሊፍቱ ጋ አግኝቼዉ አሁን''
“ማንን?” አልኋት ለወጉ፣ ማንን ማለቷ እንደሆነ ባላጣዉም፡፡
“ጀሪምን ነዋ”
“እሺ”
“ምን እሺ ትይኛለሽ? ሰላምታ ከልክሎኝ ሄደ እኮ”
“ኧረ?” አልኋት፣ ከእሽጉ ዉሃ ከፍቼ ወደ ጡጦዋ እየቀነስሁ ዉሃዉ መቼ እንደ ተቀመጠልኝ ግን አላወቅሁም: ከአጠገቡ ሶፍት፣ ፎጣ እና ሌሎች አልባሌ ነገሮችም መኖራቸዉን ሳይ ማረፊያ ክፍሉን ከመያዜ
በፊትም ተቀምጠዉ እንደነበር ገባኝ፡፡
“አይገርምሽም? መቼስ ረስቶሽ ነዉ አትዪኝም ጃሪም እኔን ሊረሳ? ጉድ እኮ ነዉ! ያኔ እንዲያ …” ብላ፣ ተገርማ ቀረች፡፡ እየቆየ እንደገና በኃይል ከነከናት፡ ምክንያቷን አላጣሁትም፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሳለን ለአንድ ዕረፍት እኛ ቤት በነበርንበት ጊዜ፣ ጃሪም ዓይን አብዝቶባት ነበር
እንዲያዉም ደጋግሞ ወድጃታለሁ እንዳለኝ አስታዉሳለሁ ስሜቱን በግልጽ ለእሷ እንደ ነገራት ግን አላውቅም፡ ከአሁኑ ሁኔታዋ
እንዳስተዋልሁት ከሆነ፣ መንገር ብቻም ሳይሆን እሞትልሻለሁ› ጭምር ሳይላት እንዳልቀረ ገመትሁ ያ ሁሉ ቀርቶ አሁን ግን እንደማያዉቃት ከሆነባት፣ ባይገርማት ነበር የሚገርመኝ፡ ያዉ፣ የእኔ ጓደኛ አይደለች?
በእሱ ቤት እኮ አሁን፣ የእኔ የሆነ እና እኔ የነካሁት ሁሉ ርኩስ
ሆኖበታል።
“አጀብ ነዉ አለ ጅብ? የሆነዉስ ይሁንና በምን ዝም አሰኘሻት?” አለች፣ ቱናትን ገለጥ እያደረገቻት፡ ከጀርባዋ አጥንት ላይ ላለዉ ቁስል ጥንቃቄ አድርጋላት፣ አቀፈቻት እና ልትቀመጥ ብትፈልግ መቀመጫ አጣች: ገና
ይኸኔ ነዉ የሆቴል ማረፊያ ክፍል ዉስጥ መሆኔ ራሱ ትዝ ያላት:
የጃሪምን ፊት መንሳት ማመን አቅቷት ዋናዉን ጥያቄዋን እንደ ረሳችዉ ልብ አደረገች፡፡
“ቆይ ቆይ፣ አንቺ ግን እዚህ ምን ትሠሪያለሽ? ከእመዋ ቤት ያዉም ያን ድግስ ጥለሽ? ያዉም ይቺን ጨቅላ ይዘሽ? ምን ልትሆኚ እዚህ መጣሽ በይ?”
ይኸዋ! እንደ ፈራሁት የማርያም መንገድ እንኳን ሳታስቀርልኝ ጥያቄዋን አመጣችዉ ያልሰማሁ መስዬ ዝም ልላት ፈልጌ ነበር፡ ነገር ግን እሷን ሽሽት ዓይኔን የጣልሁበት ባልቻም ከእሷ በላይ አፈጠጠብኝ፡፡ ለራሱ ጉዳይ
ቢሆን፣ ሽንቱ እንኳን የፈለገ ወጥሮ ቢይዘዉ የሲራክ ፯ ጉዳይ ፋታ
እንደማይሰጠዉ እያወቅሁ፣ ለእኔ ሲል ነዉ አትረፍርፎ የሚሰጠኝ። እኔ ግን እንደ ደመኛ ተደብቄዉ እዚህ ሲያገኘኝ ማዘን ይበቃዉ ይሆን? እንኳን ማኩረፍ ሌላም ቢያደርግ እዉነት አለዉ፡ ግን እሱ ነዉና ሰዉዬዉ፣ መተዉ ያዉቅበታል፡ ያም ቢሆን ግን ጥያቄዋን ተጋርቷታል።
እንድመልስላት ከእሷ እኩል እየተቁለጨለጨብኝ ሳለ እሸቴ በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ መቼ እንደ ወጣ ግን አላየሁትም ነበር፡፡ ለካንስ እመዋ ደዉላለት፣ እሷን ለማነጋገር ወጥቶ ኖሯል።
“እመዋ ናት የደወለችልኝ። (ልምጣ ወይ እያለች ነዉ፣ ትምጣ እንዴ?" አለ፣ ሳይታወቀዉ በሸዊትና
በባልቻ ከተፋጠጥሁበት ጥያቄ
ሲያስመልጠኝ፡ ባልቻ ቅር እንዳለዉም ቢሆን ቸለል አለልኝ፡ ሸዊትም እንዲሁ ቱናትን እንዳቀፈቻት ከአልጋዉ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ወተቱን ለማጥባት ሞከረች::
“እናንተ?” አለች፣ ወተቱን ልታጠጣት ሞክራ ሞክራ እንዳልሆነላት ስታዉቅ ተስፋ እየቆረጠች። “ቱናት የተለየ ልምምድ ሳያስፈልጋት
አይቀርም: ከተወለደች አንስቶ ኹለቱን ወር ሙሉ የከረመችዉ ግሉኮስ ተተክሎላት ስለነበር፣ ከጡትም ሆነ ከጡጦ ምግብ ስትሞክር ይኼ የመጀመሪያዋ ነዉ። ስለዚህ፣ እንደኔ እንደኔ አሁኑኑ ወደ ሆስፒታል ተመልሳ መግባት ያለባት ይመስለኛል” አለች፣ እኔ ደግሞ እንድሞክራት
እያቀበለችን፡ “ለጊዜዉ ጉሉኮሱም ቢሆን ማግኘት አለባት” አታዩትም
አተነፋፈሷንስ? የባሰ ሲር ሲር እያለ እኮ ነዉ። ለመሆኑ የቀጣይ
ሕክምናዋን ጉዳይ አማክራ ችሁበታል ወይ?”
“ማንን፣ ይኼዉ አንቺ አለሽል አይደል? አንቺዉ ምከሪን እጂ” አለ ባልቻ፣ እኔም እንደዚሁ ልላት ስል ቀድሞኝ፡፡
ይኼ ሙያዬ አይደለም: ስለዚህ እኔ በቅጡ ከምፈተፍት፣ ጉዳዩን ይሁነኝ ብለዉ የተማሩት
ባለሙያዎች ስላሉ ወደ እነሱ መሄድ ይኖርብናል”
«የት ናቸዉ እነሱ ታዲያ?”
“ምን እሱማ ባላውቃቸውስ በአብዛኛዉ ሆስፒታሎች አይጠፉም ነበር:: ግን የመሣሪያዎች ዉስንነት አለ: ለጊዜዉ ሕክምናዉ በኹለት
ሆስፒታሎች ብቻ እንደሚገኝ ነዉ የማዉቀዉ”
“በስመ አብ!” አለ ባልቻ፡ “ወረፋዉ አያድርስ ነዉ በይኛ''
“በጣም!”
ከመንግሥት ሆስፒታሎች መካከል ይኼን ሕመም ጉዳዬ ብሎ በብቸኝነት ሕክምና ወደሚሰጠዉ ዘዉዲቱ ሆስፒታል ሄድን፡፡ አቤት ወረፋዉ! ያሉት
አልጋዎች ዉስን ናቸዉ፤ ተመዝግቦ ተራዉን የሚጠባበቀዉ ግን የትየለሌ! እንዲያዉም የኋላ ኋላ እንደ ሰማነዉ ከሆነስ፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ብቻ ከሃያ ሺ የሚበልጡ ሕጻናት የቱናት ዓይነት እክል ያጋጥማቸዋል አሉ፡ ቁጥሩን አሰብሁት ስንት የሚወራላቸዉ
ወረርሽኞችም እኮ ከዚህ የከፉ አይደሉም
የቱናንት ሁኔታ አጣዳፊ መሆኑን ልናስረዳ ብንልም፣ የሚሰማን
አላገኘንም: አብዛኛዉ እዚህ የመጣዉ ሰዉ ሁሉ ቱናት ካለችበት የሚተናነስ አለመሆኑን አምነን ተቀበልን፡፡ ሆኖም ሕክምናዉን በተመለከተ እስከሚወሰንልን ድረስ፣ ባይሆን በረኀብ እንዳትሞትብን በሚል ግሉኮስ ተፈቅዶልን አንድ ጥግ ላይ ተተከለላት:: በረንዳ ላይ:
መኝታ ክፍልማ የሚታሰብም አይደለም፡
“በቃ እናንተ ሂዱ እጂ” አልኋቸዉ፣ ለግማሽ ሰዓት ያህል እንደዚሁ
እንደ ቆየን፡፡ እሳቱ የማይበርድ ችግር እየተጠባበቃቸዉ ሳለ፣ የሦስቱም እዚህ መቀመጥ ከቱናት ሕክምና ባልተናነሰ አሳስቦኛል ሸዊትም ፋታ የለሽ ሐኪም ናት፣ ባልቻም ባልቻ ነዉ፣ እሸቴም ያዉ ነዉ፡፡ “ሂዱ አረ! ሂዱ” አልሁኝ፣ እንደማግባባትም እንደማጣደፍም እያደረግሁ::
“መጨረሻዉን ሳንሰማ?” አለ ባልቻ፣ ስልክ ስልኩን ሲያይ እንዳልነበር ሁሉ፡
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...ሚስተር ካርላይል ወደ በሩ ሲያመራ ሮጣ ሔዳ አየችውና:
“አርኪባልድ በጣም ትቆያለህ እንዴ ? " አለችው።
“አይ ከአንድ ሰዓት የበለጠ አልቆይም ” ብሏት መልሶ በክንዶቹ እቅፍ አድርጎ ያዛት " ወዲያውም ደወለና ማርቨል መጣች።
ትጠብቀው ለነበረችው ለኮርነሊያ የማይመጣ መሆኑን እንድትነግራት ልኮ በሩን ዘጋና ሚስቱን ትክ ብሎ ሲያያት በጣም ነው የሚጨነቅልኝ ለካ ብላ አስበች " በበነጋው ጧት በቁርስ ጊዜ ኮርነሊያ አስቀድማ ቦታዋን ያዘች ቀጥለው ባልና ሚስቱ መጡ "
“ እንዴት አደርሽ...እመቤቲቱ ደኅና ተመችቶሽ አደርሽ ? ” እለቻት "
“ ደኅና ነኝ አመሰግናለሁ ” አለችና ከሚስ ካርላይል ፊት ለፊት ልትቀመጥ ስትል ያንቺ ቦታ ያ ነው...እሜቴ ” ብላ በእጅዋ ወደ ገበታው ራስጌ አመለከተቻት
ቡናውንም ፈቃድሽ ቢሆን እኔ ልቅዳልሽና ከመቅዳቱ ችግር ላድንሽ ” አለቻት።
“ ከሆነ በጣም ደስ ይለኛል ” አለች ሳቤላ።
ቁርስ ተበልቶ ሊያበቃ ሲል የሥጋ ደንበኛቸው ምን ምን ሥጋ እንደሚ
ቀርብ ለመጠየቅ መምጣቱን ፒተር ገብቶ ተናገረ መልሱ የሚጠበቀሙ ከሳቤላ ነበር።
እሷ ለራሷየዚህ ልምድ አልነበራትም " ምን እንደምትል ግራ ገብቷት ዝም አለች "
ነገረኛይቱ ኮርነሊያ ከአጠገቧ ባትኖር ኖሮ ) ከባልዋ ጋርም ቢሆን ትመካከርበት ነበር
አሁን አልቻለችም " እኅቲቱም ዝም ብላ ጠበቀቻት " ፒተርም መልስ ይዞ ለመሔድ እንደ ቆመ ቀረ
“ ጥቂት ለቅቅልና ለጥብስ የሚሆን ነገር እንዲያመጣ ብትነግረው ” አለች ሳቤላ ፈራ ተባ እያለች "
ቀስ ብላ ነበር የተናገረችው ሚስተር ካርላይልም ስለ ቤት አያያዝ ከሷ የተሻለ ስለማያውቅ የሷን ቃል ደገመው "
“ አዎን ለቅቅልና ለጥብስ የሚሆን ነገር እንዲያመጣ ለሰውየው ንግረው ፒተር አለ "
ሚስ ኮርነሊያ ብድግ አለች እንደዚህ ያለውን ትእዛዝ እየሰማች ዝም ልትል አልቻለችም " “ ለመሆኑ እንደዚህ የመሰለ ትአዛዝ ሥጋ ሻጩን ግራ እንደሚያጋባው ዐውቀሻል... እመቤት ? የሚያስፈልገውን ትእዛዝ ለዛሬ እኔ ልስጥልሽ ዓሳ ሻጩም አሁን ይመጣል ”
ከሆነስ እሺ!” ሳቤላ ከጭንቀቱ በመገላገሏ ደስ እያላት ፡ “ እኔ የዚህ ልምድ የለኝም " ወደፊት ግን የግድ መማር አለብኝ ስለ ቤት አያያዝ ምንም ነገር የማውቅ
አይመስለኝም
ሚስ ኮርኒ ምንም ሳትመልስላት ነጠቅ ነጠቅ ያለች ወታ ሔደች ሳቤላም ተይዛ እንደ ተለቀቀች ወፍ ከወንበሯ ብድግ አለችና ከባሏ ጎን ቆመቾ አበቃህ
አርኪባልድ ?
“ ማብቃቴ ነው የኔ ፍቅር ! ቡኖዬ ለካ ይኸው ይኸውና በቃ ጨረስኩ
እስኪ በግቢው ትንሽ ዘወር ዘወር እንበል ” አለችሙ እሱም ከተቀመጠበት ተነሣ ቀጭን ሽንጧን በእጁ አየዳበስ አስተውሎ አያት አሁን ሦስት ሰአት ዐልፏል እንደምታቂው ደግሞ አንድ ወር ሙሉ ቢሮ አልገባሁም"
እንባዋ ባይኗ ምላ ከኔ ጋር ብትቆይ ደስ ይለኝ ነበር " እኔስ ሁልጊዜ አብረከኝ መሆንክን እመኛለሁ » ኢስት ሊን ያላንተ ኢስት ሊን አይሆንም።
በተቻለ መጠን ካንቺ አልለይም
ፍቅሬ " አላት በጆሮዋ“ አሁን ነይና
በግቢው መኖፈሻ አብረን እንሸራሽር "
ወደ ክፍሏ ገብታ ለባበሰችና ተያይዘው ወጡ ካርላይል ስለ እህቷ ለማንሳት ምቹ አጋጣሚ ሆነለት "
እሷ ከእኛ ጋር ለመቀመጥ ትፈልጋለች ምዓ እንደምወስን አላወቅሁም በአንድ በኩል ቤቱን በማስተዳዶር ብዙ ልትጠቀምሽ ትችል ይሆናል " በሌላ በኩል
ደግሞ እኔና አንቺ ብቻችንን ብንሆን እንደ ልባችን ሆነን ደስ ብሎን የምንኖር ይመስልሻል?
ሳቤላ የተቋጠረ ፊቷ የማይፈታው ሚስ ኮርነሊያ ቋሚ ጠባቂ መሆኗን ስታስበው ልቧ ፍስስ አለ ግን ተጨናቂ ይሎኝተኛ ለሌሎች ስሜት አጥብቃ የምታስብ ረቂቅ ሰው ስለ ነበረች ምንም የቅሬታ ቃል አልተነፈሰችም “ ላንተና
ለሚስ ካርላይል ደስ የሚላችሁ ከሆነ ይሁን ” አለችው ላቤላ "
“ ሳቤላ .. ” አላት ኰስተር ብሎ።“እኔ የምፈልገው ላንቺ ደስ የሚልሽ እንዲሆን ነው " ማንኛውም ነገር እንደሚያስደስትሽ ሆኖ እንዲደራጅ እፈልጋለሁ
እኔ አሁን በሕይወቴ ዋናው ዓላማዬ ያንቺ ደስታ ነው ”
አባባሉ ከልቡ መሆኑን ሳቤላ ተረዳችው እሱን የመሰለ እውነተኛ ፍቅረኛና ጠባቂ ከጐኗ ካለ ሚስ ካርላይል የኑሮን ሰላም እንደማታበላሽባት ተሰማትና
ተዋት ትቀመጥ ፡ አርኪባልድ ... ምንም አታስቸግረንም ” አለችው "
“ እስቲ ለሁሉም ለአንድ ሁለት ወር ያህል ሁኔታውን እንየው ” አላት " እንዲህ እየተወያዩ ከመናፈሻው በር ደረሱና ሊለያት ሲል፡“ እኔስ ብቻዬን ወደ ቤት ከምመለስ አብሬህ ወደ ቢሮህ ሔጄ ጸሐፊህ በሆንኩ ደስ ይለኝ ነበር ' አለችው
እሱም በአነጋገሯ ሳቀና ተሰናብቷት ሔደ »
ሳቤላ ክፍሎቹን ሁሉ እየዞረች አየች » ሁሉም ጸጥ ብለዋል " ባባቷ ዘመን የነበራቸው ድምቀትና ሙቀት ጠፍቷል “ ከመልበሻ ክፍሏ ስትገባ ማርቨልን
ተንበርክካ የተጠፈረ ዕቃ ስትፈታ አየኘቻት " ሳቤላ ስትገባ ከእምብርክኳ ተነሣች
“ አንድ ጊዜ ላነጋግርዎ እሜቴ ? "
"ምንድነው?"
ማርቨል ከዚያ ሞቅ ሞቅ የማይል ትንሽና ቀዝቃዛ ግቢ መኖር ስለማይስማማት የእመቤቷ ፈቃድ ቢሆን ዕለቱን ለመሰናበት መፈለጓንና ይኸንኑም ተስፋ በማድረግ ዕቃዋን እንደ መጣ ያለ መፍታቷን ነገረቻት "
“ስለ አሽከሮቹ ጉዳይ አንድ የተፈጸመ ስሕተት ስለ አለ ነው " በተቻለ ፍጥነት ይታረማል " በተረፈ የሚስተር ካርላይል ቤት ምጥን ያለና ውሱን መሆኑን
ገና ከማግባቴ በፊት ነግሬሽ ነበር።
“ እመቤቴ እሱን ሁሉ እችለው ይሆናል ከሚስ ካርላይል ጋር ግን አንኳንም እንዲያውም ሁለት ግልፍተኞች ስንገናኝ አፍ እንዳንካፈትና ከዚያም አልፈን እጅ እንዳንሰናዘር እፈራለሁ እኔ በዚህ ዐይነት ሥፍር ቁጥር የሌለው ወርቅ ቢሰጡኝም አልቀመጥም " የዚህ ያሁኑ ሩብ ዓመት ደሞዜም ቢይዙብኝም ለመቅረት
አልፈልግም " ስለዚህ የተጠፈረውን ዕቃ ካደራጀሁልዎ በኋላ እንዲያሰናብቱኝ ብቻ
ነው የምለምነዎ "
ሳቤላ ፡ ማርቭል እንዳትሔድባት ለመለመን ክብሯ ባይፈቅድላትም ያለ ደንገጡር ምን እንደሚበጃት ሐሳብ ያዛት" ቢሆንም እርሳስና ወረቀት ይዛ የምትሰጣትን ዶሞዝ
አስልታ የብርና የወርቅ ገንዘቦች ከጠረጴዛው ላይ ካደረገችላት በኋላ ማርቨል . . ማግኘት ከሚገባሽ በላይ ነው " አስጠንቅቀሽና በቂ ጊዜ ሰጥተሽኝ መሔድ ነበረብሽ ” አለቻትና ትታት ወጣች " ማርቨልም እንዳለችው ትናንትናውን የገባውን ዕቃ አደራጅታ ስታበቃ ጆይስ እየሰደበቻትና እያዘነችባት ወጥታ ሔደች "
ሳቤላ ለምሣ ልብሷን ልትለብስ ወደ ክፍሏ ስትሔድ ጆይስ ተከትላት ገባች "
“ እኔ ለራሴ ስለ ወይዛዝርት ደንገጡርነት ልምድ የለኝም ነገር ግን ቢፋቅዱልኝ የምችለውን እንድረዳዎ ሚስ ካርላይል ልከውኝ ነው የመጣሁት አለቻት
ሳቤላ የሚስ ካርላይልን ደግነት በልቧ አመሰገነች "
“ የእቃዎችዎን ቁልፎች አምነው ከሰጡኝ እያሰብኩ አሰናዳልዎታልሁ ”
“እኔ ስለ ቁልፎች ምንም አላውቅም" ይዠም አላውቅ " አለቻት ሳቤላ ።ጆይስ የሚቻላትን ሁሉ ካደረገች በኋላ ' ሳቤላ ወደ ምግብ ቤት ወረዶች » ጊዜው
ወደ ዐሥራ ሁለት ሰዓት ተቃርቦ ነበር ፤የራት ሰዓት ማለት ነው። ሳቤላ ሚስተር ካርላይልን ሲመጣ ለማግኘት ወደ መናፈሻው በር እያዘገመች ሔደች "
ከበሩ ዐልፋ ጥቂት ራመድ ካለች በኋላ በመንገዱ ዘቅዝቃ ብትመለከት አጣችው " ስለዚህ ተመልሳ ገብታ ከመንገዱ ትይዩ ፈንጠር ብላ ከአንድ ጥላማ ዛፍ
ሥር ተቀመጠች ወራቱ የግንቦት መገባደጃ በመሆኑ በጣም ይሞቅ ነበር ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...ሚስተር ካርላይል ወደ በሩ ሲያመራ ሮጣ ሔዳ አየችውና:
“አርኪባልድ በጣም ትቆያለህ እንዴ ? " አለችው።
“አይ ከአንድ ሰዓት የበለጠ አልቆይም ” ብሏት መልሶ በክንዶቹ እቅፍ አድርጎ ያዛት " ወዲያውም ደወለና ማርቨል መጣች።
ትጠብቀው ለነበረችው ለኮርነሊያ የማይመጣ መሆኑን እንድትነግራት ልኮ በሩን ዘጋና ሚስቱን ትክ ብሎ ሲያያት በጣም ነው የሚጨነቅልኝ ለካ ብላ አስበች " በበነጋው ጧት በቁርስ ጊዜ ኮርነሊያ አስቀድማ ቦታዋን ያዘች ቀጥለው ባልና ሚስቱ መጡ "
“ እንዴት አደርሽ...እመቤቲቱ ደኅና ተመችቶሽ አደርሽ ? ” እለቻት "
“ ደኅና ነኝ አመሰግናለሁ ” አለችና ከሚስ ካርላይል ፊት ለፊት ልትቀመጥ ስትል ያንቺ ቦታ ያ ነው...እሜቴ ” ብላ በእጅዋ ወደ ገበታው ራስጌ አመለከተቻት
ቡናውንም ፈቃድሽ ቢሆን እኔ ልቅዳልሽና ከመቅዳቱ ችግር ላድንሽ ” አለቻት።
“ ከሆነ በጣም ደስ ይለኛል ” አለች ሳቤላ።
ቁርስ ተበልቶ ሊያበቃ ሲል የሥጋ ደንበኛቸው ምን ምን ሥጋ እንደሚ
ቀርብ ለመጠየቅ መምጣቱን ፒተር ገብቶ ተናገረ መልሱ የሚጠበቀሙ ከሳቤላ ነበር።
እሷ ለራሷየዚህ ልምድ አልነበራትም " ምን እንደምትል ግራ ገብቷት ዝም አለች "
ነገረኛይቱ ኮርነሊያ ከአጠገቧ ባትኖር ኖሮ ) ከባልዋ ጋርም ቢሆን ትመካከርበት ነበር
አሁን አልቻለችም " እኅቲቱም ዝም ብላ ጠበቀቻት " ፒተርም መልስ ይዞ ለመሔድ እንደ ቆመ ቀረ
“ ጥቂት ለቅቅልና ለጥብስ የሚሆን ነገር እንዲያመጣ ብትነግረው ” አለች ሳቤላ ፈራ ተባ እያለች "
ቀስ ብላ ነበር የተናገረችው ሚስተር ካርላይልም ስለ ቤት አያያዝ ከሷ የተሻለ ስለማያውቅ የሷን ቃል ደገመው "
“ አዎን ለቅቅልና ለጥብስ የሚሆን ነገር እንዲያመጣ ለሰውየው ንግረው ፒተር አለ "
ሚስ ኮርነሊያ ብድግ አለች እንደዚህ ያለውን ትእዛዝ እየሰማች ዝም ልትል አልቻለችም " “ ለመሆኑ እንደዚህ የመሰለ ትአዛዝ ሥጋ ሻጩን ግራ እንደሚያጋባው ዐውቀሻል... እመቤት ? የሚያስፈልገውን ትእዛዝ ለዛሬ እኔ ልስጥልሽ ዓሳ ሻጩም አሁን ይመጣል ”
ከሆነስ እሺ!” ሳቤላ ከጭንቀቱ በመገላገሏ ደስ እያላት ፡ “ እኔ የዚህ ልምድ የለኝም " ወደፊት ግን የግድ መማር አለብኝ ስለ ቤት አያያዝ ምንም ነገር የማውቅ
አይመስለኝም
ሚስ ኮርኒ ምንም ሳትመልስላት ነጠቅ ነጠቅ ያለች ወታ ሔደች ሳቤላም ተይዛ እንደ ተለቀቀች ወፍ ከወንበሯ ብድግ አለችና ከባሏ ጎን ቆመቾ አበቃህ
አርኪባልድ ?
“ ማብቃቴ ነው የኔ ፍቅር ! ቡኖዬ ለካ ይኸው ይኸውና በቃ ጨረስኩ
እስኪ በግቢው ትንሽ ዘወር ዘወር እንበል ” አለችሙ እሱም ከተቀመጠበት ተነሣ ቀጭን ሽንጧን በእጁ አየዳበስ አስተውሎ አያት አሁን ሦስት ሰአት ዐልፏል እንደምታቂው ደግሞ አንድ ወር ሙሉ ቢሮ አልገባሁም"
እንባዋ ባይኗ ምላ ከኔ ጋር ብትቆይ ደስ ይለኝ ነበር " እኔስ ሁልጊዜ አብረከኝ መሆንክን እመኛለሁ » ኢስት ሊን ያላንተ ኢስት ሊን አይሆንም።
በተቻለ መጠን ካንቺ አልለይም
ፍቅሬ " አላት በጆሮዋ“ አሁን ነይና
በግቢው መኖፈሻ አብረን እንሸራሽር "
ወደ ክፍሏ ገብታ ለባበሰችና ተያይዘው ወጡ ካርላይል ስለ እህቷ ለማንሳት ምቹ አጋጣሚ ሆነለት "
እሷ ከእኛ ጋር ለመቀመጥ ትፈልጋለች ምዓ እንደምወስን አላወቅሁም በአንድ በኩል ቤቱን በማስተዳዶር ብዙ ልትጠቀምሽ ትችል ይሆናል " በሌላ በኩል
ደግሞ እኔና አንቺ ብቻችንን ብንሆን እንደ ልባችን ሆነን ደስ ብሎን የምንኖር ይመስልሻል?
ሳቤላ የተቋጠረ ፊቷ የማይፈታው ሚስ ኮርነሊያ ቋሚ ጠባቂ መሆኗን ስታስበው ልቧ ፍስስ አለ ግን ተጨናቂ ይሎኝተኛ ለሌሎች ስሜት አጥብቃ የምታስብ ረቂቅ ሰው ስለ ነበረች ምንም የቅሬታ ቃል አልተነፈሰችም “ ላንተና
ለሚስ ካርላይል ደስ የሚላችሁ ከሆነ ይሁን ” አለችው ላቤላ "
“ ሳቤላ .. ” አላት ኰስተር ብሎ።“እኔ የምፈልገው ላንቺ ደስ የሚልሽ እንዲሆን ነው " ማንኛውም ነገር እንደሚያስደስትሽ ሆኖ እንዲደራጅ እፈልጋለሁ
እኔ አሁን በሕይወቴ ዋናው ዓላማዬ ያንቺ ደስታ ነው ”
አባባሉ ከልቡ መሆኑን ሳቤላ ተረዳችው እሱን የመሰለ እውነተኛ ፍቅረኛና ጠባቂ ከጐኗ ካለ ሚስ ካርላይል የኑሮን ሰላም እንደማታበላሽባት ተሰማትና
ተዋት ትቀመጥ ፡ አርኪባልድ ... ምንም አታስቸግረንም ” አለችው "
“ እስቲ ለሁሉም ለአንድ ሁለት ወር ያህል ሁኔታውን እንየው ” አላት " እንዲህ እየተወያዩ ከመናፈሻው በር ደረሱና ሊለያት ሲል፡“ እኔስ ብቻዬን ወደ ቤት ከምመለስ አብሬህ ወደ ቢሮህ ሔጄ ጸሐፊህ በሆንኩ ደስ ይለኝ ነበር ' አለችው
እሱም በአነጋገሯ ሳቀና ተሰናብቷት ሔደ »
ሳቤላ ክፍሎቹን ሁሉ እየዞረች አየች » ሁሉም ጸጥ ብለዋል " ባባቷ ዘመን የነበራቸው ድምቀትና ሙቀት ጠፍቷል “ ከመልበሻ ክፍሏ ስትገባ ማርቨልን
ተንበርክካ የተጠፈረ ዕቃ ስትፈታ አየኘቻት " ሳቤላ ስትገባ ከእምብርክኳ ተነሣች
“ አንድ ጊዜ ላነጋግርዎ እሜቴ ? "
"ምንድነው?"
ማርቨል ከዚያ ሞቅ ሞቅ የማይል ትንሽና ቀዝቃዛ ግቢ መኖር ስለማይስማማት የእመቤቷ ፈቃድ ቢሆን ዕለቱን ለመሰናበት መፈለጓንና ይኸንኑም ተስፋ በማድረግ ዕቃዋን እንደ መጣ ያለ መፍታቷን ነገረቻት "
“ስለ አሽከሮቹ ጉዳይ አንድ የተፈጸመ ስሕተት ስለ አለ ነው " በተቻለ ፍጥነት ይታረማል " በተረፈ የሚስተር ካርላይል ቤት ምጥን ያለና ውሱን መሆኑን
ገና ከማግባቴ በፊት ነግሬሽ ነበር።
“ እመቤቴ እሱን ሁሉ እችለው ይሆናል ከሚስ ካርላይል ጋር ግን አንኳንም እንዲያውም ሁለት ግልፍተኞች ስንገናኝ አፍ እንዳንካፈትና ከዚያም አልፈን እጅ እንዳንሰናዘር እፈራለሁ እኔ በዚህ ዐይነት ሥፍር ቁጥር የሌለው ወርቅ ቢሰጡኝም አልቀመጥም " የዚህ ያሁኑ ሩብ ዓመት ደሞዜም ቢይዙብኝም ለመቅረት
አልፈልግም " ስለዚህ የተጠፈረውን ዕቃ ካደራጀሁልዎ በኋላ እንዲያሰናብቱኝ ብቻ
ነው የምለምነዎ "
ሳቤላ ፡ ማርቭል እንዳትሔድባት ለመለመን ክብሯ ባይፈቅድላትም ያለ ደንገጡር ምን እንደሚበጃት ሐሳብ ያዛት" ቢሆንም እርሳስና ወረቀት ይዛ የምትሰጣትን ዶሞዝ
አስልታ የብርና የወርቅ ገንዘቦች ከጠረጴዛው ላይ ካደረገችላት በኋላ ማርቨል . . ማግኘት ከሚገባሽ በላይ ነው " አስጠንቅቀሽና በቂ ጊዜ ሰጥተሽኝ መሔድ ነበረብሽ ” አለቻትና ትታት ወጣች " ማርቨልም እንዳለችው ትናንትናውን የገባውን ዕቃ አደራጅታ ስታበቃ ጆይስ እየሰደበቻትና እያዘነችባት ወጥታ ሔደች "
ሳቤላ ለምሣ ልብሷን ልትለብስ ወደ ክፍሏ ስትሔድ ጆይስ ተከትላት ገባች "
“ እኔ ለራሴ ስለ ወይዛዝርት ደንገጡርነት ልምድ የለኝም ነገር ግን ቢፋቅዱልኝ የምችለውን እንድረዳዎ ሚስ ካርላይል ልከውኝ ነው የመጣሁት አለቻት
ሳቤላ የሚስ ካርላይልን ደግነት በልቧ አመሰገነች "
“ የእቃዎችዎን ቁልፎች አምነው ከሰጡኝ እያሰብኩ አሰናዳልዎታልሁ ”
“እኔ ስለ ቁልፎች ምንም አላውቅም" ይዠም አላውቅ " አለቻት ሳቤላ ።ጆይስ የሚቻላትን ሁሉ ካደረገች በኋላ ' ሳቤላ ወደ ምግብ ቤት ወረዶች » ጊዜው
ወደ ዐሥራ ሁለት ሰዓት ተቃርቦ ነበር ፤የራት ሰዓት ማለት ነው። ሳቤላ ሚስተር ካርላይልን ሲመጣ ለማግኘት ወደ መናፈሻው በር እያዘገመች ሔደች "
ከበሩ ዐልፋ ጥቂት ራመድ ካለች በኋላ በመንገዱ ዘቅዝቃ ብትመለከት አጣችው " ስለዚህ ተመልሳ ገብታ ከመንገዱ ትይዩ ፈንጠር ብላ ከአንድ ጥላማ ዛፍ
ሥር ተቀመጠች ወራቱ የግንቦት መገባደጃ በመሆኑ በጣም ይሞቅ ነበር ።
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የክሪስቶፈርፍለጋና ውጤቶቹ
ድንገት የሆነ እጅ ትከሻዬን እየወዘወዘ ቀሰቀሰኝ! በድንጋጤና በመርበትበት እናቴ መሆኗን እንኳን መለየት ያልቻልኳት ሴት ላይ በፍርሀት አፈጠጥኩ::
መልሳ አፍጥጣብኝ እጅግ በተቆጣ ድምፅ “ወንድምሽ የት ነው?" ስትል ጠየቀችኝ፡፡
በጣም ከቁጥጥር ውጪ ሆና ስትናገር ስሰማት እንዳትመታኝ እየተሸማቀቅኩ አይኖቼን ክሪስቶፈር ወደሚተኛበት አልጋ ወረወርኩ ባዶ ነበር። አምላኬ
በጣም ብዙ ቆይቷል።
መዋሸት ይገባኝ ይሆን? ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ሄዷል ብዬ ልከላከልለት? አይሆንም እቺ እናታችን ናት፤ ትወደናለች… ትረዳናለች… “ክሪስ እዚህ ፎቅ
ላይ ያሉ ክፍሎችን ለማየት ወጥቷል” አልኩ።
ግልፅነት መልካም ነው አይደል? እርስ በርሳችን ተወሻሽተንም ሆነ ለእናታችን ዋሽተን አናውቅም፡ የምንዋሸው ለአያትየው ነው እሱም አስፈላጊ ሲሆን ብቻ።
“የተረገመ! የተረገመ! የተረገመ! ስትል እየጮኸች ወደ እኔ ባተኮረ አዲስ የቁጣ ማዕበል ነደደች ውዱ ትልቁ ልጇ፣ ከሁሉም የምታስበልጠው ልጇ፣ የዲያብሎስ ተፅዕኖ ካላረፈበት በስተቀር በጭራሽ አይከዳትም፡ ትከሻዬን ይዛ ልክ እንደሚራገፍ ጨርቅ አራገፈችኝ፡፡
“በማንኛውም ሁኔታ ሁለተኛ አንቺና ክሪስቶፈር ከዚህ ክፍል እንድትወጡ አልፈቅድላችሁም ሁለታችሁም ቃላችሁን ሰጥታችሁኝ ነበር ግን ቃላችሁን
አጠፋችሁ አሁን ታዲያ እንዴት ላምናችሁ እችላለሁ ላምናችሁ የምችል መስሎኝ ነበር የምትወዱኝና በፍፁም የማትከዱኝ ይመስለኝ ነበር!”
አይኖቼ ፈጠጡ እኛ ነን የከዳናት? እንደዚህ አይነት ሁኔታ ስላሳየችን
ደንግጫለሁ። ለእኔ እሷ የከዳችን ነው የመሰለኝ፡
“እማዬ ምንም መጥፎ ነገር አልሰራንም: የተደበቅንበት ቦታ የቆየነው በፀጥታ ነበር፡ ሰዎች በዙሪያችን ሲመጡና ሲሄዱ ነበር፡ ግን ማንም እዚያ መሆናችንን አላወቀም ማንም እዚህ እንዳለን አያውቅም: ሁለተኛ ከዚህ
አላስወጣችሁም ማለት አትችይም ከዚህ ልታስወጪን ግድ ነው፡ ለዘለዓለም እዚህ ውስጥ ልትደብቂንና ልትቆልፊብን አትችይም:” ምንም መልስ ሳትሰጠኝ በእንግዳና በንቀት አይን ተመለከተችኝ፡፡ በጥፊ የምትመታኝ መስሎኝ ነበር
ግን አላደረገችውም ትከሻዬን ለቀቀችኝና ለመውጣት ፊቷን አዞረች።
ልክ ክፍሉን ለቃ ወጥታ ራሷ ልትፈልገው ስትል በሩ ተከፈተና ወንድሜ ሹክክ ብሎ ወደ ውስጥ ገባ:: በሩን ለቀቀና ዞሮ ወደ እኔ ተመለከተ። ከዚያ ለመናገር ከንፈሩን አላቀቀ: የዚያን ጊዜ እናታችንን ሲመለከት እጅግ እንግዳ የሆነ ስሜት ፊቱ ላይ ታየ።
ለምን እንደሆነ ባላውቅም፣ እንደ ሁልጊዜው እናታችንን ሲያይ አይኖቹ በደስታ አልበሩም።
እናታችን በቅፅበት አጠገቡ ደረሰችና አንዴ በጥፊ አላሰችው: የንዴቷ ብዛት ከድንጋጤው ሳይመለስ ግራ እጇን አነሳችና ሌላኛው ጉንጩ ላይ በጥፊ
መረገችበት።
የክሪስ የገረጣ ፊት ሁለት ትልልቅ ቀያይ ምልክቶች አወጣ።
“ክሪስቶፈር ፎክስወርዝ፣ ሁለተኛ እንደዚህ አይነት ነገር ብታደርግ እኔ ራሴ ነኝ የምገርፍህ! አንተን ብቻ ሳይሆን ካቲንም ጭምር” ክሪስ የተፈጥሮ ቀለሙ ጠፍቶ ፊቱ በጥፊ የተመታበት ምልክቶች የደም አሻራዎች ሆነው
ይታዩ ነበር የራሴ ደም ወደ እግሬ ሲወርድ ከጆሮዎቼ ኋላ የሚያቃጥል ስሜት ተሰማኝ
ጥንካሬዬ እያነሰ መጥቶ እንግዳ እየመሰለች የመጣችው ሴት ላይ አፈጠጥኩ።
ልክ እንደማላውቃትና ለማወቅም ግድ የሌለኝ አይነት ሴት ሆነችብኝ፡ እውነት ይህቺ ሁልጊዜ በደግነትና በፍቅር የምታነጋግረን እናታችን ናት? ረጅም ጊዜ ተዘግቶብን በመቆየታችን የሚሰማንን ስሜት እጅግ ትረዳን የነበረችው
እናታችን ናት? ቤቱ እንደዚህ እንድትሆን የሆነ ነገር አደረጋት ይሆን? ፈጥኖ የመጣልኝ ሀሳብ ይሄ ነው ...ትንንሾቹ ነገሮች ሁሉ ተደምረው እንድትለወጥ አደረጓት
የሚለው፡ በፊት እንደምታደርገው ብዙ ጊዜ አትመጣም: መጀመሪያ አካባቢ እንደምታደርገው በቀን ሁለት ጊዜ ወይም በየቀኑ አትመጣም አሁን የምናምንበትና የምንጠጋበት ነገር ሁሉ ከእግራችን ስር ሾልኮ፣ ሁሉን ነገር አጥተን አሻንጉሊቶች፣ መጫወቻዎችና ስጦታዎች
ብቻ የቀሩን ስለመሰለኝ ፈራሁ።
በክሪስ የደነገጠ ፊት ላይ ንዴቷን የሚያጠፋ የሆነ ነገር አይታ መሆን አለበት በክንዶቿ አቅፋ የጎዳችውን ለመካስ በጥፊ ተመትቶ የቀላውን ፊቱን
በችኮላና በትንንሹ በመሳም ልታፅናናው ሞከረች። ሳመችው፣ ሳመችው፣ሳመችው ፀጉሩን በጣቶቿ አበጠረች ጉንጮቹን አሻሸች: ጭንቅላቱን ወደ ጡቶቿ አስጠግታ አቀፈችው
“ይቅርታ አድርግልኝ ውዴ” አይኖቿና ድምፅዋ ውስጥ እምባ አለ፡ “ይቅር በለኝ… እባክህ ይቅር በለኝ. ስለ መግረፍ ያወራሁት ከልቤ አይደለም:እንዴት እኔን ልትፈራኝ ትችላለህ? እወድሀለሁ እኮ ታውቃለህ አንተንም
ሆነ ካቲን በጭራሽ አልገርፋችሁም: ገርፌያችሁ አውቃለሁ? ራሴን ስላልሆንኩ ነው እንደዚያ የተናገርኩት። ሁሉም ነገር ባሰብኩት መንገድ
እየሄደልን ስለሆነ ያንን ለማበላሸት ምንም ነገር ማድረግ ስለሌለባችሁ ነው በጥፊ የተማታሁበት ብቸኛው ምክንያት ያ ብቻ ነው።” አለችው:
ፊቱን በመዳፎቿ መሀል ጥብቅ አድርጋ ይዛ፣ የተጨማደደ ፊቱን እያየች ጉንጩ ላይ ሳመችው: የሆነ ስሜት እየተሰማኝ ቁጭ ብዬ በመገረም እየተመለከትኩ ነበር… ግራ ከመጋባቴና ልጅ ከመሆኔ ውጪ ምን እየተሰማኝ እንደሆነ አላውቅም በዙሪያችን ያለው አለም ግን በሙሉ ያረጀ በጣም
ያረጀ ነበር።
ይቅርታ አደረገላት በእርግጥም ምን እየተካሄደ እንደሆነ ማወቅ አለብን። “እባክሽ እማዬ፣ ምን እንደሆነ ንገሪን እባክሽ?”
“ሌላ ጊዜ” አለች ወደ ዳንሱ ለመመለስ ጥድፊያ ላይ ነበረች: ሁለታችንንም እንደገና ሳመችን፡ “ሌላ ጊዜ ምናልባት ነገ ሁሉንም ነገር እነግራችኋለሁ"አለችና በችኮላ እየሳመችን የሚያፅናኑ ቃላት ነገረችን: በእኔ ላይ ተንጠራርታ ኬሪን ሳመቻት ከዚያ ወደ ኮሪ ሄዳ ጉንጩን ሳመች።
“ይቅር ብለኸኛል ክሪስቶፈር?”
“አዎ እማዬ፤ ልክ ነሽ እዚሁ ክፍል ነው መቀመጥ ያለብን ለማየት መውጣት አይገባኝም ነበር”
ፈገግ አለችና “መልካም የገና በዓል፣ በቅርቡ አያችኋለሁ:" ከዚያ ወጣችና በሩን ቆልፋ ሄደች።
እዚህ ከመጣን ያሳለፍነው የመጀመሪያው የገና በዓላችን አለቀ: አዳራሹ ውስጥ ያለው ሰዓት ሰባት ሰዓት መሆኑን አመለከተ: በስጦታ የተሞላ
ክፍል፣ ቲቪ፣ የጠየቅነው የቼዝ መጫወቻ፣ የሚሞቁ አዳዲስ ልብሶችና ብዙ የሚበሉ ጣፋጮች ነበሩን፡፡ እኔና ክሪስ ደግሞ አስገራሚ ግብዣ ነበረን
ሆኖም የሆነ አዲስ ነገር ወደ ህይወታችን መጥቷል የማናውቀው አዲሱ
የእናታችን ባህርይ ለአጭር ደቂቃ እናታችን ልክ አያታችንን መስላ ነበር።
በጨለማ አንድ አልጋ ላይ በአንደኛው ጎን ኬሪ፣ በሌላው ጎን ክሪስ ተኝቶ እኔና ክሪስ እጅ ለእጅ ተያይዘናል፡ ጠረኑ ከእኔ የተለየ ነው ጭንቅላቴ ደረቱ ላይ አርፏል። ከሩቅ ወደ ጆሯችን ከሚመጣው በትንሹ ከሚሰማው ሙዚቃ
“ ልቡ ሲመታ ይሰማኛል ፀጉሬን በጣቶቹ እያፍተለተለ ነበር።
ክሪስ ትልቅ ሰው መሆን በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው አይደል?"
“ይመስለኛል”
“ትልቅ ሰው ስትሆን የትኛውንም አይነት ሁኔታ መቋቋም እንደምትችል አስባለሁ መቼም ቢሆን ስህተትና ትክክል ለሆነው ነገር ጥርጣሬ ገብቶህ አያውቅም ትልልቅ ሰዎች እንደኛ ይፍጨረጨራሉ ብዬ አልገምትም
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የክሪስቶፈርፍለጋና ውጤቶቹ
ድንገት የሆነ እጅ ትከሻዬን እየወዘወዘ ቀሰቀሰኝ! በድንጋጤና በመርበትበት እናቴ መሆኗን እንኳን መለየት ያልቻልኳት ሴት ላይ በፍርሀት አፈጠጥኩ::
መልሳ አፍጥጣብኝ እጅግ በተቆጣ ድምፅ “ወንድምሽ የት ነው?" ስትል ጠየቀችኝ፡፡
በጣም ከቁጥጥር ውጪ ሆና ስትናገር ስሰማት እንዳትመታኝ እየተሸማቀቅኩ አይኖቼን ክሪስቶፈር ወደሚተኛበት አልጋ ወረወርኩ ባዶ ነበር። አምላኬ
በጣም ብዙ ቆይቷል።
መዋሸት ይገባኝ ይሆን? ጣሪያው ስር ወዳለው ክፍል ሄዷል ብዬ ልከላከልለት? አይሆንም እቺ እናታችን ናት፤ ትወደናለች… ትረዳናለች… “ክሪስ እዚህ ፎቅ
ላይ ያሉ ክፍሎችን ለማየት ወጥቷል” አልኩ።
ግልፅነት መልካም ነው አይደል? እርስ በርሳችን ተወሻሽተንም ሆነ ለእናታችን ዋሽተን አናውቅም፡ የምንዋሸው ለአያትየው ነው እሱም አስፈላጊ ሲሆን ብቻ።
“የተረገመ! የተረገመ! የተረገመ! ስትል እየጮኸች ወደ እኔ ባተኮረ አዲስ የቁጣ ማዕበል ነደደች ውዱ ትልቁ ልጇ፣ ከሁሉም የምታስበልጠው ልጇ፣ የዲያብሎስ ተፅዕኖ ካላረፈበት በስተቀር በጭራሽ አይከዳትም፡ ትከሻዬን ይዛ ልክ እንደሚራገፍ ጨርቅ አራገፈችኝ፡፡
“በማንኛውም ሁኔታ ሁለተኛ አንቺና ክሪስቶፈር ከዚህ ክፍል እንድትወጡ አልፈቅድላችሁም ሁለታችሁም ቃላችሁን ሰጥታችሁኝ ነበር ግን ቃላችሁን
አጠፋችሁ አሁን ታዲያ እንዴት ላምናችሁ እችላለሁ ላምናችሁ የምችል መስሎኝ ነበር የምትወዱኝና በፍፁም የማትከዱኝ ይመስለኝ ነበር!”
አይኖቼ ፈጠጡ እኛ ነን የከዳናት? እንደዚህ አይነት ሁኔታ ስላሳየችን
ደንግጫለሁ። ለእኔ እሷ የከዳችን ነው የመሰለኝ፡
“እማዬ ምንም መጥፎ ነገር አልሰራንም: የተደበቅንበት ቦታ የቆየነው በፀጥታ ነበር፡ ሰዎች በዙሪያችን ሲመጡና ሲሄዱ ነበር፡ ግን ማንም እዚያ መሆናችንን አላወቀም ማንም እዚህ እንዳለን አያውቅም: ሁለተኛ ከዚህ
አላስወጣችሁም ማለት አትችይም ከዚህ ልታስወጪን ግድ ነው፡ ለዘለዓለም እዚህ ውስጥ ልትደብቂንና ልትቆልፊብን አትችይም:” ምንም መልስ ሳትሰጠኝ በእንግዳና በንቀት አይን ተመለከተችኝ፡፡ በጥፊ የምትመታኝ መስሎኝ ነበር
ግን አላደረገችውም ትከሻዬን ለቀቀችኝና ለመውጣት ፊቷን አዞረች።
ልክ ክፍሉን ለቃ ወጥታ ራሷ ልትፈልገው ስትል በሩ ተከፈተና ወንድሜ ሹክክ ብሎ ወደ ውስጥ ገባ:: በሩን ለቀቀና ዞሮ ወደ እኔ ተመለከተ። ከዚያ ለመናገር ከንፈሩን አላቀቀ: የዚያን ጊዜ እናታችንን ሲመለከት እጅግ እንግዳ የሆነ ስሜት ፊቱ ላይ ታየ።
ለምን እንደሆነ ባላውቅም፣ እንደ ሁልጊዜው እናታችንን ሲያይ አይኖቹ በደስታ አልበሩም።
እናታችን በቅፅበት አጠገቡ ደረሰችና አንዴ በጥፊ አላሰችው: የንዴቷ ብዛት ከድንጋጤው ሳይመለስ ግራ እጇን አነሳችና ሌላኛው ጉንጩ ላይ በጥፊ
መረገችበት።
የክሪስ የገረጣ ፊት ሁለት ትልልቅ ቀያይ ምልክቶች አወጣ።
“ክሪስቶፈር ፎክስወርዝ፣ ሁለተኛ እንደዚህ አይነት ነገር ብታደርግ እኔ ራሴ ነኝ የምገርፍህ! አንተን ብቻ ሳይሆን ካቲንም ጭምር” ክሪስ የተፈጥሮ ቀለሙ ጠፍቶ ፊቱ በጥፊ የተመታበት ምልክቶች የደም አሻራዎች ሆነው
ይታዩ ነበር የራሴ ደም ወደ እግሬ ሲወርድ ከጆሮዎቼ ኋላ የሚያቃጥል ስሜት ተሰማኝ
ጥንካሬዬ እያነሰ መጥቶ እንግዳ እየመሰለች የመጣችው ሴት ላይ አፈጠጥኩ።
ልክ እንደማላውቃትና ለማወቅም ግድ የሌለኝ አይነት ሴት ሆነችብኝ፡ እውነት ይህቺ ሁልጊዜ በደግነትና በፍቅር የምታነጋግረን እናታችን ናት? ረጅም ጊዜ ተዘግቶብን በመቆየታችን የሚሰማንን ስሜት እጅግ ትረዳን የነበረችው
እናታችን ናት? ቤቱ እንደዚህ እንድትሆን የሆነ ነገር አደረጋት ይሆን? ፈጥኖ የመጣልኝ ሀሳብ ይሄ ነው ...ትንንሾቹ ነገሮች ሁሉ ተደምረው እንድትለወጥ አደረጓት
የሚለው፡ በፊት እንደምታደርገው ብዙ ጊዜ አትመጣም: መጀመሪያ አካባቢ እንደምታደርገው በቀን ሁለት ጊዜ ወይም በየቀኑ አትመጣም አሁን የምናምንበትና የምንጠጋበት ነገር ሁሉ ከእግራችን ስር ሾልኮ፣ ሁሉን ነገር አጥተን አሻንጉሊቶች፣ መጫወቻዎችና ስጦታዎች
ብቻ የቀሩን ስለመሰለኝ ፈራሁ።
በክሪስ የደነገጠ ፊት ላይ ንዴቷን የሚያጠፋ የሆነ ነገር አይታ መሆን አለበት በክንዶቿ አቅፋ የጎዳችውን ለመካስ በጥፊ ተመትቶ የቀላውን ፊቱን
በችኮላና በትንንሹ በመሳም ልታፅናናው ሞከረች። ሳመችው፣ ሳመችው፣ሳመችው ፀጉሩን በጣቶቿ አበጠረች ጉንጮቹን አሻሸች: ጭንቅላቱን ወደ ጡቶቿ አስጠግታ አቀፈችው
“ይቅርታ አድርግልኝ ውዴ” አይኖቿና ድምፅዋ ውስጥ እምባ አለ፡ “ይቅር በለኝ… እባክህ ይቅር በለኝ. ስለ መግረፍ ያወራሁት ከልቤ አይደለም:እንዴት እኔን ልትፈራኝ ትችላለህ? እወድሀለሁ እኮ ታውቃለህ አንተንም
ሆነ ካቲን በጭራሽ አልገርፋችሁም: ገርፌያችሁ አውቃለሁ? ራሴን ስላልሆንኩ ነው እንደዚያ የተናገርኩት። ሁሉም ነገር ባሰብኩት መንገድ
እየሄደልን ስለሆነ ያንን ለማበላሸት ምንም ነገር ማድረግ ስለሌለባችሁ ነው በጥፊ የተማታሁበት ብቸኛው ምክንያት ያ ብቻ ነው።” አለችው:
ፊቱን በመዳፎቿ መሀል ጥብቅ አድርጋ ይዛ፣ የተጨማደደ ፊቱን እያየች ጉንጩ ላይ ሳመችው: የሆነ ስሜት እየተሰማኝ ቁጭ ብዬ በመገረም እየተመለከትኩ ነበር… ግራ ከመጋባቴና ልጅ ከመሆኔ ውጪ ምን እየተሰማኝ እንደሆነ አላውቅም በዙሪያችን ያለው አለም ግን በሙሉ ያረጀ በጣም
ያረጀ ነበር።
ይቅርታ አደረገላት በእርግጥም ምን እየተካሄደ እንደሆነ ማወቅ አለብን። “እባክሽ እማዬ፣ ምን እንደሆነ ንገሪን እባክሽ?”
“ሌላ ጊዜ” አለች ወደ ዳንሱ ለመመለስ ጥድፊያ ላይ ነበረች: ሁለታችንንም እንደገና ሳመችን፡ “ሌላ ጊዜ ምናልባት ነገ ሁሉንም ነገር እነግራችኋለሁ"አለችና በችኮላ እየሳመችን የሚያፅናኑ ቃላት ነገረችን: በእኔ ላይ ተንጠራርታ ኬሪን ሳመቻት ከዚያ ወደ ኮሪ ሄዳ ጉንጩን ሳመች።
“ይቅር ብለኸኛል ክሪስቶፈር?”
“አዎ እማዬ፤ ልክ ነሽ እዚሁ ክፍል ነው መቀመጥ ያለብን ለማየት መውጣት አይገባኝም ነበር”
ፈገግ አለችና “መልካም የገና በዓል፣ በቅርቡ አያችኋለሁ:" ከዚያ ወጣችና በሩን ቆልፋ ሄደች።
እዚህ ከመጣን ያሳለፍነው የመጀመሪያው የገና በዓላችን አለቀ: አዳራሹ ውስጥ ያለው ሰዓት ሰባት ሰዓት መሆኑን አመለከተ: በስጦታ የተሞላ
ክፍል፣ ቲቪ፣ የጠየቅነው የቼዝ መጫወቻ፣ የሚሞቁ አዳዲስ ልብሶችና ብዙ የሚበሉ ጣፋጮች ነበሩን፡፡ እኔና ክሪስ ደግሞ አስገራሚ ግብዣ ነበረን
ሆኖም የሆነ አዲስ ነገር ወደ ህይወታችን መጥቷል የማናውቀው አዲሱ
የእናታችን ባህርይ ለአጭር ደቂቃ እናታችን ልክ አያታችንን መስላ ነበር።
በጨለማ አንድ አልጋ ላይ በአንደኛው ጎን ኬሪ፣ በሌላው ጎን ክሪስ ተኝቶ እኔና ክሪስ እጅ ለእጅ ተያይዘናል፡ ጠረኑ ከእኔ የተለየ ነው ጭንቅላቴ ደረቱ ላይ አርፏል። ከሩቅ ወደ ጆሯችን ከሚመጣው በትንሹ ከሚሰማው ሙዚቃ
“ ልቡ ሲመታ ይሰማኛል ፀጉሬን በጣቶቹ እያፍተለተለ ነበር።
ክሪስ ትልቅ ሰው መሆን በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው አይደል?"
“ይመስለኛል”
“ትልቅ ሰው ስትሆን የትኛውንም አይነት ሁኔታ መቋቋም እንደምትችል አስባለሁ መቼም ቢሆን ስህተትና ትክክል ለሆነው ነገር ጥርጣሬ ገብቶህ አያውቅም ትልልቅ ሰዎች እንደኛ ይፍጨረጨራሉ ብዬ አልገምትም
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
‹‹አይሮፕላኑን ባህሩ ላይ እንድጥለው ትፈልጋለህ?››
‹‹እንደዚያማ ማድረግ አትችልምº እኔ አይሮፕላኑ ውስጥ አለሁ
ፓይለቱ እዚያ ቦታ ላይ በድንገት እንዲያርፍ የሚያስገድደው አንድ ችግር ፍጠር›› አለው በሚገባ በተከረከመ ጥፍሩ ፖስት ካርዱ ላይ ያለውን ቦታ እያመለከተው፡፡
የበረራ መሃንዲሱ ፓይለቱ በድንገት አይሮፕላኑን ለማሳረፍ የሚያስገድደው ችግር መፍጠር አያቅተውም፡፡ ነገር ግን አይሮፕላኑን የሚያሳርፍ ችግር መፍጠር ለጊዜው ኤዲ አልከሰትልህ አለው፡፡
‹‹ቀላል እንዳልሆነ ይገባኛል፤ ነገር ግን የማይሆን ነገር ግን አይደለም
እኔም ይህን ማድረግ እንደሚቻል አረጋግጫለሁ››
‹‹ማነው ይህን የነገረህ? እናንተስ እነማን ናችሁ? አለ ኤዲ ንዴቱ ተቀስቅሶ፡
‹‹ትዕዛዝ መፈጸም እንጂ መጠየቅ አትችልም›› አለው ሉተር::
ኤዲ መጀመሪያ ሉተርን ሊያስፈራራው ሞከረ፣ አሁን ግን አቅመ ቢስ ሆኗል፡ አሁን በፍርሃት መሸበብ የእሱ ተራ ሆኗል፡ ሉተር ይህን ጉዳይ በሚገባ ያቀደ የወሮበላ ቡድን አባል ነው፡፡ ኤዲን ለእኩይ ተግባራቸው
በመሳሪያነት ሊጠቀሙበት ነው የመረጡት፡ ውጥናቸውን ዳር ለማድረስ
ደግሞ ካሮል አንን እመዳፋቸው ስር አውለዋታል፡
ኤዲ ፖስት ካርዱን ኪሱ ከተተና ትተባበራለህ ወይስ አትተባበርም?›› ሲል ሉተር በጉጉት ጠየቀ፡፡
ኤዲ ዞር አለና አፈጠጠበት፡ ከዚያም መልስ ሳይሰጥ መንገዱን ቀጠለ፡
ኤዲ በጠላቶቹ ፊት ፈርጠም ያለ ባህሪ ለማሳየት ቢሞክርም እውነታው ግን እንዳንበረከኩት ነው የሚያሳየው እነዚህ ወሮበሎች ለምንድነው ይህን ማድረግ የፈለጉት? ባንድ ወቅት ጀርመኖች ቦይንግ 314 አይሮፕላንን
ሰርቀው ዲዛይኑን ኮፒ ለማድረግ ፈልገው እንደነበር ያውቃል፡ አሁን ይህን ማድረግ ቢፈልጉ አይሮፕላኑን ሜይን ስቴት ውስጥ ሳይሆን አውሮፓ
ውስጥም ሰርቀው መውሰድ የሚያግዳቸው ነገር የለም፡፡
አይሮፕላኑን በሚፈልጉበት ቦታ ላይ እንዲወርድ ለማድረግ ማሰባቸው
ቦታው ላይ የሚጠብቅ ጀልባ እንዳላቸው ይጠቁማል፡ ‹ግን ለምን?› ሉተር ሻንጣ ሙሉ ሃሺሽ፣ ባዙቃ፣ ኮሚኒስት አብዮተኛ ወይስ የናዚ ሰላይ ነው
ወደ አሜሪካ ማስገባት የፈለገው? እነ ሉተር እዚህ ችግር ውስጥ ለመግባት
የወሰኑት መቼም ሊያስገቡት ያሰቡት ሰው ወይም ነገር በጣም ጠቃሚ
ስለሆነ ነው፡፡
ኤዲ ከሌሎቹ የስራ ባልደረቦቹ ይልቅ እሱን የመረጡበት ምክንያት
አሁን ገብቶታል፡አይሮፕላኑን አንድ ቦታ በድንገት እንዲያርፍ ከተፈለገ
ይህን ማድረግ የሚችለው የበረራ መሀንዲሱ ነው፡፡ ናቪጌተሩ ምንም ማድረግ አይችልም የሬዲዮ ኦፕሬተሩም እንዲሁ፤ ፓይለቱ ደግሞ የረዳት
ፓይለቱ ድጋፍ ያስፈልገዋል፡ የበረራ መሀንዲሱ ግን ብቻውን
የአይሮፕላኑን ሞተር ቀጥ ሊያደርገው ይችላል፡፡
ሉተር የፓን አሜሪካንን አየር መንገድ መሀንዲሶች ስም ዝርዝር ሳያገኝ አልቀረም፡ ስም ዝርዝሩንም ማግኘት ከባድ አይደለም:፡ የአየር መንገዱን መረጃ ለማየት አንድ ምሽት ላይ አንዱ የሉተር ጓደኛ የአየር መንገዱን ቢሮ ሰብሮም ቢሆን ሊያገኘው ይችላል ወይም አንዷን ጸሐፊ በጉቦ መደለል ነው፡፡ ለምን ግን ኤዲን መረጡ? ሉተር በዚህ ቀን የሚበረው የበረራ
መሃንዲስ ስም እጁ ገብቷል ከዚያም ኤዲ ለዚህ ሰይጣናዊ ተግባር
እንዲሆን ለማድረግ ሲያስብ አንድ መላ ያገኛል፤ ሚስቱን ማገት፡፡
እነዚህን ወንበዴዎች መርዳት ለኤዲ ልብ የሚሰብር ጉዳይ ሆኖበታል፡
ወንበዴዎች እጣ ክፍሎቹ አይደሉም፡ ሰርተው ከማግኘት ይልቅ ሌት ተቀን
ከሚለፉ ሰዎች አፍ እየነጠቁና እያጭበረበሩ ተንደላቀው ይኖራሉ፡ ህግ
አክባሪ ሰዎች የዕለት እንጀራ ለማግኘት ጀርባቸው ሲጎብጥ ይውላል፡ እነዚህ
ማፊያዎች ግን ለፍቶ አዳሪዎች ላይ ሽጉጥ እየደገኑ፣ ለፍተው ያገኙትን
ተሽከርካሪዎች ያሽከረክራሉ፡፡ እነዚህን ወንጀለኞች በኤሌክትሪክ ወንበር ላይ ጠፍሮ በኮረንቲ እያንጨረጨሩ መግደል ነው የሚያዋጣው፡፡
ቶም ሉተርን ማሞኘት ቀላል አይደለም፡፡ ሚስቱን ካሮል አንን አግቷታል። ሉተር ያቀደውን ትልም ኤዲ ለማደናቀፍ ሞከረ ማለት በሚስቱ አንገት ላይ የታሰረውን ገመድ ሸምቀቆ አጠበቀ ማለት ነው፡፡ ሊያታልላቸው
ወይም ሊታገላቸው አይችልም፤ ያሉትን ከመፈጸም ውጭ፡
ሆዱን እንደጨነቀው ከወደቡ ወጥቶ በመንደሩ ያለችውን ብቸኛ መንገድ አቋርጦ ወደ አንድ ሆቴል ሄደ፡ ሆቴሉ እንዳለ የተያዘው በፓን አሜሪካን አየር መንገድ ሰራተኞች ነው ማለት ይቻላል፡፡ እዚያም ካፒቴን ቤከርና ረዳቱ ጆኒ ዶት ከፓን አሜሪካ የፎየንስ ጣቢያ ኃላፊ ጋር የራዲዮ
መልእክቶችን እየገመገሙ የአትላንቲክ አቋራጭን በረራ ስለማድረግና አለማድረግ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ ጉባኤ በተቀመጡበት ክፍል ኤዲ ገብቶ ተሰየመ፡
በአይሮፕላን በረራ ሳይንስ ቁልፍ ጉዳይ የነፋሱ ጥንካሬ ነው፡፡ ወደ ምዕራብ ሲጓዙ ከጠንካራው ነፋስ ጋር እየታገሉ ነው በረራው የሚካሄደው፡ ከፊት ለፊት የሚመጣውን የንፋስ ግፊት ለመሸሽ ሲሉ ፓይለቶች
በተደጋጋሚ ከፍታቸውን ለመለዋወጥ ይገደዳሉ፡ ይህም ቴክኒክ በበረራው
ሳይንስ ‹ነፋሱን ማሳደድ›› ይባላል፡ ዝቅተኛ ቦታ ላይ ያለ ነፋስ ግፊቱ ያነሰ
ቢሆንም አይሮፕላኑ ዝቅ እያለ በበረረ ቁጥር ከመርከብ ወይም ባህር ላይ ከሚዋልል የበረዶ ቋጥኝ ጋር ሊላተም ይችላል፡፡ ከፊት ለፊት የሚመጣን ንፋስ ግፊት ለመቋቋም በርካታ ነዳጅ ማቃጠል ይጠይቃል፡ ኃይለኛ የንፋስ ግፊት ካለ ከአይርላንድ እስከ ኒውፋውንድ ላንድ (ካናዳ) ከሁለት ሺህ ማይል
በላይ ለመብረር የሚበቃ ነዳጅ አይሮፕላኑ መያዝ ስለማይችል የነዳጅ
እጥረት ሊያጋጥም ይችላል፡ በዚህም ምክንያት በረራው ለሌላ ቀን ሊተላለፍ
ስለሚችል የአየሩ ጠባይ እስከሚሻሻል ተጓዦች በሆቴል ሊቆዩ የሚችሉበት
አጋጣሚ ይፈጠራል፡
የዚህ ዓይነት የአየር መዛባት ቢከሰት ካሮል አንን ምን ይውጣት ይሆን?
የአየር ጠባይ ሪፖርቱ ነፋሱ ከባድ መሆኑን፣ አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ደግሞ ከባድ ማዕበል እንዳለ ያመለክታል፡፡ አይሮፕላኑ ሙሉ ሰው ጭኗል፡
ስለዚህ ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ሁሉ ነገር በጥንቃቄ መሰላት አለበት፡፡ የአየሩ
ጠባይ መጥፎ መሆን የኤዲን ጭንቀት አባባሰው፡፡ ሚስቱ ካሮል አን በወዲያኛው የውቅያኖስ ጥግ በጨካኝ ወንበዴዎች እጅ ወድቃ እሱ እዚህ አየርላንድ ውስጥ ተጣብቆ መቅረቱን
ሊቋቋመው የሚችለው ነገር
አይደለም፡፡ ለመሆኑ ምግብ ይሰጧት ይሆን? የምትተኛበት ቦታስ አላት
ይሆን? ብርድስ ይመታት ይሆን?› እያለ ያስባል።
የአትላንቲክ ውቅያኖስን አካባቢ የሚያሳየው ማፕ ጋ ሄደና ቶም ሉተር የሰጠውን አይሮፕላኑ እንዲያርፍበት የሚፈለግበትን ቦታ ተመለከተ፡፡ ቦታው
ተጠንቶ የተመረጠ ነው ከካናዳ ጠረፍ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቆ ቤይ አፍ
ፈንዲ› የሚባል በጠረፉና በአንድ ትንሽ ደሴት መካከል የሚገኝ ቦታ ነው:
ምንም እንኳን ባህር ላይ ለሚያርፉ አይሮፕላኖች ማረፊያነቱ ብዙም
ተመራጭ ባይሆንም ከገላጣው የባህር ክፍል የተሻለ ነው፡፡ ይህን ሲያውቅ ኤዲ ተስፋው ለመለመ፡ ቢያንስ የማረፉ ነገር ብዙ ችግር የለውም፡፡ ሉተር ሚስቱን በእጁ እንዲያስገባለትና እቅዱ እንዲሳካ አቅሙን በሙሉ አሟጧዐየተጣለበትን ግዴታ መወጣት አለበት፡
አሁንም ግን አይሮፕላኑን እዚያ ቦታ እንዴት ሊያሳርፍ እንደሚችልዐመጨነቁ አልቀረም፡ በዚህ ቦታ እንዲያርፍ ያደረኩት አንዱ የአይሮፕላኑ ሞተር ስለተበላሽ ነው ቢል በሶስት ሞተር ሊሄድ እንደሚችል ረዳት የበረራ መሀንዲሱ ሚኪ ፊን ስለሚያውቅ ይህ ምክንያት ብዙም አያስኬድም የአዕምሮውን ጓዳ ቢያስስም ተጨባጭ መፍትሄ አልመጣለት አለ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_በወንዳየሁ_ንጉሴ
‹‹አይሮፕላኑን ባህሩ ላይ እንድጥለው ትፈልጋለህ?››
‹‹እንደዚያማ ማድረግ አትችልምº እኔ አይሮፕላኑ ውስጥ አለሁ
ፓይለቱ እዚያ ቦታ ላይ በድንገት እንዲያርፍ የሚያስገድደው አንድ ችግር ፍጠር›› አለው በሚገባ በተከረከመ ጥፍሩ ፖስት ካርዱ ላይ ያለውን ቦታ እያመለከተው፡፡
የበረራ መሃንዲሱ ፓይለቱ በድንገት አይሮፕላኑን ለማሳረፍ የሚያስገድደው ችግር መፍጠር አያቅተውም፡፡ ነገር ግን አይሮፕላኑን የሚያሳርፍ ችግር መፍጠር ለጊዜው ኤዲ አልከሰትልህ አለው፡፡
‹‹ቀላል እንዳልሆነ ይገባኛል፤ ነገር ግን የማይሆን ነገር ግን አይደለም
እኔም ይህን ማድረግ እንደሚቻል አረጋግጫለሁ››
‹‹ማነው ይህን የነገረህ? እናንተስ እነማን ናችሁ? አለ ኤዲ ንዴቱ ተቀስቅሶ፡
‹‹ትዕዛዝ መፈጸም እንጂ መጠየቅ አትችልም›› አለው ሉተር::
ኤዲ መጀመሪያ ሉተርን ሊያስፈራራው ሞከረ፣ አሁን ግን አቅመ ቢስ ሆኗል፡ አሁን በፍርሃት መሸበብ የእሱ ተራ ሆኗል፡ ሉተር ይህን ጉዳይ በሚገባ ያቀደ የወሮበላ ቡድን አባል ነው፡፡ ኤዲን ለእኩይ ተግባራቸው
በመሳሪያነት ሊጠቀሙበት ነው የመረጡት፡ ውጥናቸውን ዳር ለማድረስ
ደግሞ ካሮል አንን እመዳፋቸው ስር አውለዋታል፡
ኤዲ ፖስት ካርዱን ኪሱ ከተተና ትተባበራለህ ወይስ አትተባበርም?›› ሲል ሉተር በጉጉት ጠየቀ፡፡
ኤዲ ዞር አለና አፈጠጠበት፡ ከዚያም መልስ ሳይሰጥ መንገዱን ቀጠለ፡
ኤዲ በጠላቶቹ ፊት ፈርጠም ያለ ባህሪ ለማሳየት ቢሞክርም እውነታው ግን እንዳንበረከኩት ነው የሚያሳየው እነዚህ ወሮበሎች ለምንድነው ይህን ማድረግ የፈለጉት? ባንድ ወቅት ጀርመኖች ቦይንግ 314 አይሮፕላንን
ሰርቀው ዲዛይኑን ኮፒ ለማድረግ ፈልገው እንደነበር ያውቃል፡ አሁን ይህን ማድረግ ቢፈልጉ አይሮፕላኑን ሜይን ስቴት ውስጥ ሳይሆን አውሮፓ
ውስጥም ሰርቀው መውሰድ የሚያግዳቸው ነገር የለም፡፡
አይሮፕላኑን በሚፈልጉበት ቦታ ላይ እንዲወርድ ለማድረግ ማሰባቸው
ቦታው ላይ የሚጠብቅ ጀልባ እንዳላቸው ይጠቁማል፡ ‹ግን ለምን?› ሉተር ሻንጣ ሙሉ ሃሺሽ፣ ባዙቃ፣ ኮሚኒስት አብዮተኛ ወይስ የናዚ ሰላይ ነው
ወደ አሜሪካ ማስገባት የፈለገው? እነ ሉተር እዚህ ችግር ውስጥ ለመግባት
የወሰኑት መቼም ሊያስገቡት ያሰቡት ሰው ወይም ነገር በጣም ጠቃሚ
ስለሆነ ነው፡፡
ኤዲ ከሌሎቹ የስራ ባልደረቦቹ ይልቅ እሱን የመረጡበት ምክንያት
አሁን ገብቶታል፡አይሮፕላኑን አንድ ቦታ በድንገት እንዲያርፍ ከተፈለገ
ይህን ማድረግ የሚችለው የበረራ መሀንዲሱ ነው፡፡ ናቪጌተሩ ምንም ማድረግ አይችልም የሬዲዮ ኦፕሬተሩም እንዲሁ፤ ፓይለቱ ደግሞ የረዳት
ፓይለቱ ድጋፍ ያስፈልገዋል፡ የበረራ መሀንዲሱ ግን ብቻውን
የአይሮፕላኑን ሞተር ቀጥ ሊያደርገው ይችላል፡፡
ሉተር የፓን አሜሪካንን አየር መንገድ መሀንዲሶች ስም ዝርዝር ሳያገኝ አልቀረም፡ ስም ዝርዝሩንም ማግኘት ከባድ አይደለም:፡ የአየር መንገዱን መረጃ ለማየት አንድ ምሽት ላይ አንዱ የሉተር ጓደኛ የአየር መንገዱን ቢሮ ሰብሮም ቢሆን ሊያገኘው ይችላል ወይም አንዷን ጸሐፊ በጉቦ መደለል ነው፡፡ ለምን ግን ኤዲን መረጡ? ሉተር በዚህ ቀን የሚበረው የበረራ
መሃንዲስ ስም እጁ ገብቷል ከዚያም ኤዲ ለዚህ ሰይጣናዊ ተግባር
እንዲሆን ለማድረግ ሲያስብ አንድ መላ ያገኛል፤ ሚስቱን ማገት፡፡
እነዚህን ወንበዴዎች መርዳት ለኤዲ ልብ የሚሰብር ጉዳይ ሆኖበታል፡
ወንበዴዎች እጣ ክፍሎቹ አይደሉም፡ ሰርተው ከማግኘት ይልቅ ሌት ተቀን
ከሚለፉ ሰዎች አፍ እየነጠቁና እያጭበረበሩ ተንደላቀው ይኖራሉ፡ ህግ
አክባሪ ሰዎች የዕለት እንጀራ ለማግኘት ጀርባቸው ሲጎብጥ ይውላል፡ እነዚህ
ማፊያዎች ግን ለፍቶ አዳሪዎች ላይ ሽጉጥ እየደገኑ፣ ለፍተው ያገኙትን
ተሽከርካሪዎች ያሽከረክራሉ፡፡ እነዚህን ወንጀለኞች በኤሌክትሪክ ወንበር ላይ ጠፍሮ በኮረንቲ እያንጨረጨሩ መግደል ነው የሚያዋጣው፡፡
ቶም ሉተርን ማሞኘት ቀላል አይደለም፡፡ ሚስቱን ካሮል አንን አግቷታል። ሉተር ያቀደውን ትልም ኤዲ ለማደናቀፍ ሞከረ ማለት በሚስቱ አንገት ላይ የታሰረውን ገመድ ሸምቀቆ አጠበቀ ማለት ነው፡፡ ሊያታልላቸው
ወይም ሊታገላቸው አይችልም፤ ያሉትን ከመፈጸም ውጭ፡
ሆዱን እንደጨነቀው ከወደቡ ወጥቶ በመንደሩ ያለችውን ብቸኛ መንገድ አቋርጦ ወደ አንድ ሆቴል ሄደ፡ ሆቴሉ እንዳለ የተያዘው በፓን አሜሪካን አየር መንገድ ሰራተኞች ነው ማለት ይቻላል፡፡ እዚያም ካፒቴን ቤከርና ረዳቱ ጆኒ ዶት ከፓን አሜሪካ የፎየንስ ጣቢያ ኃላፊ ጋር የራዲዮ
መልእክቶችን እየገመገሙ የአትላንቲክ አቋራጭን በረራ ስለማድረግና አለማድረግ ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ ጉባኤ በተቀመጡበት ክፍል ኤዲ ገብቶ ተሰየመ፡
በአይሮፕላን በረራ ሳይንስ ቁልፍ ጉዳይ የነፋሱ ጥንካሬ ነው፡፡ ወደ ምዕራብ ሲጓዙ ከጠንካራው ነፋስ ጋር እየታገሉ ነው በረራው የሚካሄደው፡ ከፊት ለፊት የሚመጣውን የንፋስ ግፊት ለመሸሽ ሲሉ ፓይለቶች
በተደጋጋሚ ከፍታቸውን ለመለዋወጥ ይገደዳሉ፡ ይህም ቴክኒክ በበረራው
ሳይንስ ‹ነፋሱን ማሳደድ›› ይባላል፡ ዝቅተኛ ቦታ ላይ ያለ ነፋስ ግፊቱ ያነሰ
ቢሆንም አይሮፕላኑ ዝቅ እያለ በበረረ ቁጥር ከመርከብ ወይም ባህር ላይ ከሚዋልል የበረዶ ቋጥኝ ጋር ሊላተም ይችላል፡፡ ከፊት ለፊት የሚመጣን ንፋስ ግፊት ለመቋቋም በርካታ ነዳጅ ማቃጠል ይጠይቃል፡ ኃይለኛ የንፋስ ግፊት ካለ ከአይርላንድ እስከ ኒውፋውንድ ላንድ (ካናዳ) ከሁለት ሺህ ማይል
በላይ ለመብረር የሚበቃ ነዳጅ አይሮፕላኑ መያዝ ስለማይችል የነዳጅ
እጥረት ሊያጋጥም ይችላል፡ በዚህም ምክንያት በረራው ለሌላ ቀን ሊተላለፍ
ስለሚችል የአየሩ ጠባይ እስከሚሻሻል ተጓዦች በሆቴል ሊቆዩ የሚችሉበት
አጋጣሚ ይፈጠራል፡
የዚህ ዓይነት የአየር መዛባት ቢከሰት ካሮል አንን ምን ይውጣት ይሆን?
የአየር ጠባይ ሪፖርቱ ነፋሱ ከባድ መሆኑን፣ አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ደግሞ ከባድ ማዕበል እንዳለ ያመለክታል፡፡ አይሮፕላኑ ሙሉ ሰው ጭኗል፡
ስለዚህ ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ሁሉ ነገር በጥንቃቄ መሰላት አለበት፡፡ የአየሩ
ጠባይ መጥፎ መሆን የኤዲን ጭንቀት አባባሰው፡፡ ሚስቱ ካሮል አን በወዲያኛው የውቅያኖስ ጥግ በጨካኝ ወንበዴዎች እጅ ወድቃ እሱ እዚህ አየርላንድ ውስጥ ተጣብቆ መቅረቱን
ሊቋቋመው የሚችለው ነገር
አይደለም፡፡ ለመሆኑ ምግብ ይሰጧት ይሆን? የምትተኛበት ቦታስ አላት
ይሆን? ብርድስ ይመታት ይሆን?› እያለ ያስባል።
የአትላንቲክ ውቅያኖስን አካባቢ የሚያሳየው ማፕ ጋ ሄደና ቶም ሉተር የሰጠውን አይሮፕላኑ እንዲያርፍበት የሚፈለግበትን ቦታ ተመለከተ፡፡ ቦታው
ተጠንቶ የተመረጠ ነው ከካናዳ ጠረፍ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቆ ቤይ አፍ
ፈንዲ› የሚባል በጠረፉና በአንድ ትንሽ ደሴት መካከል የሚገኝ ቦታ ነው:
ምንም እንኳን ባህር ላይ ለሚያርፉ አይሮፕላኖች ማረፊያነቱ ብዙም
ተመራጭ ባይሆንም ከገላጣው የባህር ክፍል የተሻለ ነው፡፡ ይህን ሲያውቅ ኤዲ ተስፋው ለመለመ፡ ቢያንስ የማረፉ ነገር ብዙ ችግር የለውም፡፡ ሉተር ሚስቱን በእጁ እንዲያስገባለትና እቅዱ እንዲሳካ አቅሙን በሙሉ አሟጧዐየተጣለበትን ግዴታ መወጣት አለበት፡
አሁንም ግን አይሮፕላኑን እዚያ ቦታ እንዴት ሊያሳርፍ እንደሚችልዐመጨነቁ አልቀረም፡ በዚህ ቦታ እንዲያርፍ ያደረኩት አንዱ የአይሮፕላኑ ሞተር ስለተበላሽ ነው ቢል በሶስት ሞተር ሊሄድ እንደሚችል ረዳት የበረራ መሀንዲሱ ሚኪ ፊን ስለሚያውቅ ይህ ምክንያት ብዙም አያስኬድም የአዕምሮውን ጓዳ ቢያስስም ተጨባጭ መፍትሄ አልመጣለት አለ፡፡
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፡ በሰላም አብረው እንዲኖሩ ከብርሃን ወደ ጨጎጎታሙ ጨጓራዬ ውስጥ አስገብቻቸው እነሱ ተባብረው እኔን አንደማጥቃት እርስ በርሳቸው ካልተስማሙና ከተጣሉ የከፋው ተበደልሁ ባይ በሁለት መንገድ (በጁ ምልክት እያሳያት
ወይም በላይ ወይ በታች መውጣት ይችላል። እኔ ደድግሞ በጠየቁኝ
አቅጣጫ በሬን እከፍታለሁ" ብሎ ፈገገ፤ ካርለት ግን ሳቋን መቆጣጠርን ተሳናት፡ ወርቃማ ፀጉሯ እስኪርገፈገፍ ተሳፋሪው ሁሉ እየዞረ እስኪያያት… ሳቀች እሱ ግን ፀጥ አለ፤ እንቅልፍ እንቅልፍ አለው ተኛ! ካርለት ትከሻ ላይ፤ ወርቃማ ፀጉሯ እንደ በቆሉ ጭራ ፊቱን ሲነካካው የናቱን ጡት እንደሚጠባ ህፃን ፍርክስክስ ብሎ ተኛ
“ኩርር… ኩርርር. እያደረገ፡፡
ዝዋይ ላይ አውቶቡስ ለቁርስ ሲቆም ነቃ። ከጠዋቱ አራት ሰዓት ተኩል ነው: ሰዉ ሁሉ ወረደ: ካርለት ካለፂማሙ ሰው
የምታውቀው የለም:: ስለዚሀ አብረው ወረዱ፡፡
የኢትዮጵያውያን ምግብ ለሷ አዲስ አይደለም። ግን
ለተወሰኑ ወራት እርቃው ቆይታለች፡፡
እሱ ጥሬ ክትፎ እሷ ዳቦና ሻይ አዘው ሲበሉ ቆዩና፡-
“ስለ ከቡ ነገርኩሽ" አለ ፂሞ:
“ማነች ከቡ?"
“ሚስቴi ለጋብቻ ስጠይቃት ፂማም ነህ' ብላ ናቀችኝ፡ ዝም ብዬ ጥረቴን ቀጠልሁ፡፡ ፂሙ አያስጠላሽም፤ምኑን ልትስሚው ነው' ብለው ሲያጥላሉባትም እኔ ጥረቴን እንደቀጠልሁ ነበር፡ አንድ
ቀን ታድያ ተሳካልኝ ለትዳር እንደምፈልጋት የተማርሁ መሆኔን ላዬ ሞኛ ሞኝ ቢሆንም ውስጤ ግን ዘመናዊ እንደሆነ በአለማችን ካሉ በጣት ከሚቆጠሩ ደስተኞች መካከል አንዱ መሆኔን…
እየዘረዘርሁ ሳጫውታት ቆየሁ፡፡ ምኗ ሞኝ መሰለችሽ! ቆቅ ነች:
ከምታየውና ከሰማችው ጋር እኔ ያልኋት ሁሉ ተምታታባት ከቡ!
“ሰርቲፍኬቴን ስቀበል የተነሳሁትን ፎቶ ሳሳያት ግን ውሃ ሆነች፡ ፍንጥር ፍንጥር ማለቷን ቀነሰች፡ ያኔ ጠልፎ እሚጥላትን ምላሴን እያወናጨፍሁ እግሯን አንስቼ እግሬ ላይ አደረግሁና የርግብ
አሳሳም ስሚያት ወጥቼ ስሄድ የጨው መላሾ እንደቀመሰ ከብት
እየተከተለችኝ ለምን አትመጣም መሰለሽ!" ብሎ ሳቁን ለቀቀው፡፡
ካርለት ስለ አንድ ነገር መናገር በጀመረ ቁጥር መጨረሻው አስቂኝ
መሆኑን መጠበቅ ጀምራ ስለነበር እሷም አብራው
ሳቀችና የሆነ ነገር
በህሊናዋ ትዝ አላት እንግዳ አባባል፡
“ምንድነው የርግብ አሳሳም''
“አታውቂም? ብዙው ኧረ በጠቅላላው ሰው የሚያውቅ አይመስለኝም" አላትና ቀና አለ፡፡ “እኔ ግን የተማርሁት ከርግቦች
ነው፡፡ ቆርቆሮዬ ላይ ሲ
ሲዳሩ አይቼ፡፡
“ታያለሽ ከንፈሬ አካባቢ ያለውን ፂሜን ለመሳም ከፈለግሁ ከሴቷ አፍ ውስጥ ገብቶ ጉሮሮዋን ያንቃታል፡፡ እኔ ደግሞ ችግር
መፍጠር አልወድም፤ ለምን ብዬ! ሰው ሁሉ የሌላው ሳይጨመር የራሱ ችግር መቼ አነሰው… ስለዚህ እኔ እንደ እርግብ አፌን
ስከፍትላት ክቡ ከንፈሯን ውስጥ ትጨምረዋለች ያኔ እጠባታለሁ ከንፈሯን: ያ ነው የእርግብ አሳሳም! ያ የርግብ አሳሳም ነው ነው
ከቡዬን እንደ ከብት እያንደረደረ እቤቴ ያስገባት፡፡ ፂሜ ችግር
ስለማይፈጥርባት ቅቤ እየቀባች ሽሩባ ትሰራኝ ጀመር፡፡ ከዚያ እንዲያውም ልቧ እየራራ እንደ ሰናፍጭ የሚሰነፍጥ ፍቅሯን
እየመገበች ይኸው ያየኝን ሁሉ አጠገብህ ካልተቀመጥን' እያስኘ
የሚያስጎመጅ ሰው ወጣኝ" አላትና ሳቀ ተሳሳቁ…..
አውቶብሱ እንደገና ጉዙውን ሲቀጥል ፂሞ ከያይነቱ
ጎንጨት አድርጎ ተኛ: ካርለት እንግዳ ባህሪው ገርሟታል። አጠገቡ
መቀመጧን እንዳልጠላችው አሁን ግን ከነበረው ሰው
ልትግባባው የምትችለው ከሱ የተሻለ እንዳልነበር ተሰማት።
አውቶብሱ የላንጋኖንና የሻላን ደን እያቆራረጠ ሲጓዝ ሙቀቱ እየጨመረ የዳቦ መጋገሪያ ፍም ላይ የተቀመጡ ያህል
ያተኩስ ጀመር። የአውቶብሱ መስኮትና በር ባጠቃላይ ክርችም ብሎ
ተዘግቶ ህዝቡ በላብ ሻወር ይታጠባል፡ መስኮቱን ለምን
እንደማይከፍቱት ፂሞን ጠይቃው የአውቶብስ መስኮት አትክፈቱ•
ብርድ ይመታችኋል ያለው ዶክተር ባይታወቅም ልጅ አዋቂውን ቃሉን አክብሮ በሙቀት መቀቀል መምረጡን ነግሯታል፡ ስለዚህ የለበሰችውን ጃኬት አውልቃ በነጭ ቲሸርት ሆና የሙቀት ቅጣቷን
እየተቀበለች ለማረፍ ከፊት ለፊቷ ካለው ወንበር የብረት ዘንግ ላይ ራሷን ደገፍ አደረገች፡፡
ሙዚቃው ማንቧረቁ አልቆመም፡፡ አውቶብሱ ማርሹን እየቀያየረ ይጓዛል፡ ካርለት እንደ ቀልድ እንቅልፍ ወስዷት ቆይታ የአውቶብሱ ሹፌር አህያ ድንገት ልትገባበት ስትል ፍሬኑን ያዝ
ሲያደርግ ከወንበሩ ጋር ተጋጨችና ብንን ብላ ደንግጣ ተነሳች፡፡
ፂሞ ያነባል። ብጥስጥስ ያለች መጽሐፉን፡ ትንሽ ቆይቶ ከትልቁ ኪሱ ወረቀቶች ያወጣና ያነብ ጀመር፡ ካርለት
ተደንቃ አየችው፡፡ ልታምን አልቻለችም፡፡ ማንም ሰው ያደርገዋል ብላም አትገምትም፡:
የምን ወረቀቶች ናቸው?”
“ወረቀቶቹ አያቸው ግንባሩን ሽቅብ ሰብሰብ አድርጎ፡፡
"ቁም ነገር ያላቸው ወረቀቶች ናቸው፡፡"
ላያቸው እኮ ቆሻሻ አለባቸው?”
“አዎ አይነምድር አው፡ ግን ደርቋል፡፡ ሳነሳው እንኳን ብዙም አልደረቀም ነበር፡ ይኸ ጃኬት ግን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለመሃረቤና
ስለሚፈጥር እዚያው ደረቀ፡፡
ለወረቀቶችም ሙቀት
እስክርቢቶ አይበረክትልኝም ሙቀቱ ያገነፍለዋል፡፡"
“ወረቀቶቹን ከየት ነው ያገኘሃቸው?''።
“በየሄድሁበት መፀዳዳትም ባልፈልግ ሽንት ቤት መሄድ
አዘወትራለሁ የተፃፈውን ማንበብ ሱስ ሆኖብኛል፡ አሁን አሁን ደግሞ አንዳንድ ሽንት ቤቶች ውስጥ ያሉ ቅርጫቶች ላይ ሰው
ተፀዳድቶባቸው እማገኛቸው ወረቀቶች ሽንት ቤቶች ከመፀዳጃነት
አልፈው ወደ መፃህፍት ቤትነት እየተቀየሩ ነው
የሚያሰኝ ነው፡፡
“በአማርኛ ሆነ እንጂ ይህን ብታነቢው የወደቅሽበትን
ሳታውቂው ሶስት ቀን ተኝተሽ ትከርሚ ነበር" አላት፡፡
“ቆሻሻ ወረቀቱን አትጠየፍም?"
“እጠየፋለሁ እንጂ! ግን ጠቃሚ ነገር ኣለበት፡፡ ጠቃሚ ነገር ደግሞ ቆሻሻ አለው ተብለቀ አይጣልም፡፡ ቆሻሻ ማለት ጥቅም
የማይሰጥ ተራ ነገር ነው፡፡
“ይገርምሻል ካለ እነዚህ'' ጀሪካኖቹን ጠቁሞ አሳያት
“...ካለ እነዚህና ካለ ከቡ የረባም ጓደኛ የለኝ፡፡ ምናልባት እኔ ወይ እነሱ ቆሻሻ ስለሆን ይሆናል ከብዙው የሥራ ጓደኞቼ ጋር
የማልግባባው ታዲያልሽ…" የትንሽዋን ጀሪካን ክዳን ከፍቶ ወደ መስታዋቱ ዞሮ አንደቀደቀና
“…ታዲያልሽ ከሽንት ቤት ቅርጫት ቆሻሻ ወረቀት አንስተህ እንዴት እኪስህ ትከታለህ ያሳዝናል! ይህን የሚፈጽም ህሊናው
የተስተካከለ ሰው የለም ካለ እብድ በቀር' ብለው አጥላሉኝ፡፡
“አንድ ቀን ታድያ ሁለት ቀያይ ብሮችን ይዥ ሽንት ቤት ገባሁና በብሩ ተፀዳጅቼ ወጣሁ፡፡ ከኔ የሚቀጥለው አላየኝም ገባ ብሎ ሲወጣ ተመልሼ ብገባ የተፀዳዳሁባቸውን የብር ኖቶች ወስዷቸዋል
ደሞ ሌላ ቦታ ሄጄ በሁለት አምስት አምስት ብሮች ተፀዳዳሁ ... ቀጥሎ የገባው ሲወጣ ብሮቹ የሉም፡፡ hዚያ ደግሞ በአንድ አንድ ብር ሞከርኩ፤ እነሱም ተወሰዱ ታዲያልሽ!ብሮቹ ከእለት ጥቅም
ሌላ ጠቃሚ አይደሉም፤ ማንም ሰው ግን ቆሽሸው ቢያገኛቸውም ወደ ኪሱ ይላቸዋል፡፡
“እና እኔ ለይወት ጠቃሚ ቁም ነገር ያለውን ቆሻሻ ወደ
ኪሴ ብል ያለፋሁበትን ገንዘብን ፈልጌ አይደል? እውቀት ጠምቶኝ
እንጂ፡፡ ስለዚህ ምኑ ያስነውራል" ከት ከት ብሎ ሳቀ፡ ካርለት አንገቷን በአድናቆት ወዘወዘች፤ አልሳቀችም፡፡
“ኢትዮጵያ ውስጥ የፍልስፍና ሰዎችም አሉ፡፡ ማህበረሰቡ ግን እንደ ቆሻሻ ያያቸዋል፧ እነሱ ግን ለአገሪቱ ጠቃሚ እሴቶች
ነበሩ…" የትልቁ ጀሪካን ክዳን እንደገና ተከፈተ፡፡ ደቅ ደቅደቅ…
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
“እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፡ በሰላም አብረው እንዲኖሩ ከብርሃን ወደ ጨጎጎታሙ ጨጓራዬ ውስጥ አስገብቻቸው እነሱ ተባብረው እኔን አንደማጥቃት እርስ በርሳቸው ካልተስማሙና ከተጣሉ የከፋው ተበደልሁ ባይ በሁለት መንገድ (በጁ ምልክት እያሳያት
ወይም በላይ ወይ በታች መውጣት ይችላል። እኔ ደድግሞ በጠየቁኝ
አቅጣጫ በሬን እከፍታለሁ" ብሎ ፈገገ፤ ካርለት ግን ሳቋን መቆጣጠርን ተሳናት፡ ወርቃማ ፀጉሯ እስኪርገፈገፍ ተሳፋሪው ሁሉ እየዞረ እስኪያያት… ሳቀች እሱ ግን ፀጥ አለ፤ እንቅልፍ እንቅልፍ አለው ተኛ! ካርለት ትከሻ ላይ፤ ወርቃማ ፀጉሯ እንደ በቆሉ ጭራ ፊቱን ሲነካካው የናቱን ጡት እንደሚጠባ ህፃን ፍርክስክስ ብሎ ተኛ
“ኩርር… ኩርርር. እያደረገ፡፡
ዝዋይ ላይ አውቶቡስ ለቁርስ ሲቆም ነቃ። ከጠዋቱ አራት ሰዓት ተኩል ነው: ሰዉ ሁሉ ወረደ: ካርለት ካለፂማሙ ሰው
የምታውቀው የለም:: ስለዚሀ አብረው ወረዱ፡፡
የኢትዮጵያውያን ምግብ ለሷ አዲስ አይደለም። ግን
ለተወሰኑ ወራት እርቃው ቆይታለች፡፡
እሱ ጥሬ ክትፎ እሷ ዳቦና ሻይ አዘው ሲበሉ ቆዩና፡-
“ስለ ከቡ ነገርኩሽ" አለ ፂሞ:
“ማነች ከቡ?"
“ሚስቴi ለጋብቻ ስጠይቃት ፂማም ነህ' ብላ ናቀችኝ፡ ዝም ብዬ ጥረቴን ቀጠልሁ፡፡ ፂሙ አያስጠላሽም፤ምኑን ልትስሚው ነው' ብለው ሲያጥላሉባትም እኔ ጥረቴን እንደቀጠልሁ ነበር፡ አንድ
ቀን ታድያ ተሳካልኝ ለትዳር እንደምፈልጋት የተማርሁ መሆኔን ላዬ ሞኛ ሞኝ ቢሆንም ውስጤ ግን ዘመናዊ እንደሆነ በአለማችን ካሉ በጣት ከሚቆጠሩ ደስተኞች መካከል አንዱ መሆኔን…
እየዘረዘርሁ ሳጫውታት ቆየሁ፡፡ ምኗ ሞኝ መሰለችሽ! ቆቅ ነች:
ከምታየውና ከሰማችው ጋር እኔ ያልኋት ሁሉ ተምታታባት ከቡ!
“ሰርቲፍኬቴን ስቀበል የተነሳሁትን ፎቶ ሳሳያት ግን ውሃ ሆነች፡ ፍንጥር ፍንጥር ማለቷን ቀነሰች፡ ያኔ ጠልፎ እሚጥላትን ምላሴን እያወናጨፍሁ እግሯን አንስቼ እግሬ ላይ አደረግሁና የርግብ
አሳሳም ስሚያት ወጥቼ ስሄድ የጨው መላሾ እንደቀመሰ ከብት
እየተከተለችኝ ለምን አትመጣም መሰለሽ!" ብሎ ሳቁን ለቀቀው፡፡
ካርለት ስለ አንድ ነገር መናገር በጀመረ ቁጥር መጨረሻው አስቂኝ
መሆኑን መጠበቅ ጀምራ ስለነበር እሷም አብራው
ሳቀችና የሆነ ነገር
በህሊናዋ ትዝ አላት እንግዳ አባባል፡
“ምንድነው የርግብ አሳሳም''
“አታውቂም? ብዙው ኧረ በጠቅላላው ሰው የሚያውቅ አይመስለኝም" አላትና ቀና አለ፡፡ “እኔ ግን የተማርሁት ከርግቦች
ነው፡፡ ቆርቆሮዬ ላይ ሲ
ሲዳሩ አይቼ፡፡
“ታያለሽ ከንፈሬ አካባቢ ያለውን ፂሜን ለመሳም ከፈለግሁ ከሴቷ አፍ ውስጥ ገብቶ ጉሮሮዋን ያንቃታል፡፡ እኔ ደግሞ ችግር
መፍጠር አልወድም፤ ለምን ብዬ! ሰው ሁሉ የሌላው ሳይጨመር የራሱ ችግር መቼ አነሰው… ስለዚህ እኔ እንደ እርግብ አፌን
ስከፍትላት ክቡ ከንፈሯን ውስጥ ትጨምረዋለች ያኔ እጠባታለሁ ከንፈሯን: ያ ነው የእርግብ አሳሳም! ያ የርግብ አሳሳም ነው ነው
ከቡዬን እንደ ከብት እያንደረደረ እቤቴ ያስገባት፡፡ ፂሜ ችግር
ስለማይፈጥርባት ቅቤ እየቀባች ሽሩባ ትሰራኝ ጀመር፡፡ ከዚያ እንዲያውም ልቧ እየራራ እንደ ሰናፍጭ የሚሰነፍጥ ፍቅሯን
እየመገበች ይኸው ያየኝን ሁሉ አጠገብህ ካልተቀመጥን' እያስኘ
የሚያስጎመጅ ሰው ወጣኝ" አላትና ሳቀ ተሳሳቁ…..
አውቶብሱ እንደገና ጉዙውን ሲቀጥል ፂሞ ከያይነቱ
ጎንጨት አድርጎ ተኛ: ካርለት እንግዳ ባህሪው ገርሟታል። አጠገቡ
መቀመጧን እንዳልጠላችው አሁን ግን ከነበረው ሰው
ልትግባባው የምትችለው ከሱ የተሻለ እንዳልነበር ተሰማት።
አውቶብሱ የላንጋኖንና የሻላን ደን እያቆራረጠ ሲጓዝ ሙቀቱ እየጨመረ የዳቦ መጋገሪያ ፍም ላይ የተቀመጡ ያህል
ያተኩስ ጀመር። የአውቶብሱ መስኮትና በር ባጠቃላይ ክርችም ብሎ
ተዘግቶ ህዝቡ በላብ ሻወር ይታጠባል፡ መስኮቱን ለምን
እንደማይከፍቱት ፂሞን ጠይቃው የአውቶብስ መስኮት አትክፈቱ•
ብርድ ይመታችኋል ያለው ዶክተር ባይታወቅም ልጅ አዋቂውን ቃሉን አክብሮ በሙቀት መቀቀል መምረጡን ነግሯታል፡ ስለዚህ የለበሰችውን ጃኬት አውልቃ በነጭ ቲሸርት ሆና የሙቀት ቅጣቷን
እየተቀበለች ለማረፍ ከፊት ለፊቷ ካለው ወንበር የብረት ዘንግ ላይ ራሷን ደገፍ አደረገች፡፡
ሙዚቃው ማንቧረቁ አልቆመም፡፡ አውቶብሱ ማርሹን እየቀያየረ ይጓዛል፡ ካርለት እንደ ቀልድ እንቅልፍ ወስዷት ቆይታ የአውቶብሱ ሹፌር አህያ ድንገት ልትገባበት ስትል ፍሬኑን ያዝ
ሲያደርግ ከወንበሩ ጋር ተጋጨችና ብንን ብላ ደንግጣ ተነሳች፡፡
ፂሞ ያነባል። ብጥስጥስ ያለች መጽሐፉን፡ ትንሽ ቆይቶ ከትልቁ ኪሱ ወረቀቶች ያወጣና ያነብ ጀመር፡ ካርለት
ተደንቃ አየችው፡፡ ልታምን አልቻለችም፡፡ ማንም ሰው ያደርገዋል ብላም አትገምትም፡:
የምን ወረቀቶች ናቸው?”
“ወረቀቶቹ አያቸው ግንባሩን ሽቅብ ሰብሰብ አድርጎ፡፡
"ቁም ነገር ያላቸው ወረቀቶች ናቸው፡፡"
ላያቸው እኮ ቆሻሻ አለባቸው?”
“አዎ አይነምድር አው፡ ግን ደርቋል፡፡ ሳነሳው እንኳን ብዙም አልደረቀም ነበር፡ ይኸ ጃኬት ግን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለመሃረቤና
ስለሚፈጥር እዚያው ደረቀ፡፡
ለወረቀቶችም ሙቀት
እስክርቢቶ አይበረክትልኝም ሙቀቱ ያገነፍለዋል፡፡"
“ወረቀቶቹን ከየት ነው ያገኘሃቸው?''።
“በየሄድሁበት መፀዳዳትም ባልፈልግ ሽንት ቤት መሄድ
አዘወትራለሁ የተፃፈውን ማንበብ ሱስ ሆኖብኛል፡ አሁን አሁን ደግሞ አንዳንድ ሽንት ቤቶች ውስጥ ያሉ ቅርጫቶች ላይ ሰው
ተፀዳድቶባቸው እማገኛቸው ወረቀቶች ሽንት ቤቶች ከመፀዳጃነት
አልፈው ወደ መፃህፍት ቤትነት እየተቀየሩ ነው
የሚያሰኝ ነው፡፡
“በአማርኛ ሆነ እንጂ ይህን ብታነቢው የወደቅሽበትን
ሳታውቂው ሶስት ቀን ተኝተሽ ትከርሚ ነበር" አላት፡፡
“ቆሻሻ ወረቀቱን አትጠየፍም?"
“እጠየፋለሁ እንጂ! ግን ጠቃሚ ነገር ኣለበት፡፡ ጠቃሚ ነገር ደግሞ ቆሻሻ አለው ተብለቀ አይጣልም፡፡ ቆሻሻ ማለት ጥቅም
የማይሰጥ ተራ ነገር ነው፡፡
“ይገርምሻል ካለ እነዚህ'' ጀሪካኖቹን ጠቁሞ አሳያት
“...ካለ እነዚህና ካለ ከቡ የረባም ጓደኛ የለኝ፡፡ ምናልባት እኔ ወይ እነሱ ቆሻሻ ስለሆን ይሆናል ከብዙው የሥራ ጓደኞቼ ጋር
የማልግባባው ታዲያልሽ…" የትንሽዋን ጀሪካን ክዳን ከፍቶ ወደ መስታዋቱ ዞሮ አንደቀደቀና
“…ታዲያልሽ ከሽንት ቤት ቅርጫት ቆሻሻ ወረቀት አንስተህ እንዴት እኪስህ ትከታለህ ያሳዝናል! ይህን የሚፈጽም ህሊናው
የተስተካከለ ሰው የለም ካለ እብድ በቀር' ብለው አጥላሉኝ፡፡
“አንድ ቀን ታድያ ሁለት ቀያይ ብሮችን ይዥ ሽንት ቤት ገባሁና በብሩ ተፀዳጅቼ ወጣሁ፡፡ ከኔ የሚቀጥለው አላየኝም ገባ ብሎ ሲወጣ ተመልሼ ብገባ የተፀዳዳሁባቸውን የብር ኖቶች ወስዷቸዋል
ደሞ ሌላ ቦታ ሄጄ በሁለት አምስት አምስት ብሮች ተፀዳዳሁ ... ቀጥሎ የገባው ሲወጣ ብሮቹ የሉም፡፡ hዚያ ደግሞ በአንድ አንድ ብር ሞከርኩ፤ እነሱም ተወሰዱ ታዲያልሽ!ብሮቹ ከእለት ጥቅም
ሌላ ጠቃሚ አይደሉም፤ ማንም ሰው ግን ቆሽሸው ቢያገኛቸውም ወደ ኪሱ ይላቸዋል፡፡
“እና እኔ ለይወት ጠቃሚ ቁም ነገር ያለውን ቆሻሻ ወደ
ኪሴ ብል ያለፋሁበትን ገንዘብን ፈልጌ አይደል? እውቀት ጠምቶኝ
እንጂ፡፡ ስለዚህ ምኑ ያስነውራል" ከት ከት ብሎ ሳቀ፡ ካርለት አንገቷን በአድናቆት ወዘወዘች፤ አልሳቀችም፡፡
“ኢትዮጵያ ውስጥ የፍልስፍና ሰዎችም አሉ፡፡ ማህበረሰቡ ግን እንደ ቆሻሻ ያያቸዋል፧ እነሱ ግን ለአገሪቱ ጠቃሚ እሴቶች
ነበሩ…" የትልቁ ጀሪካን ክዳን እንደገና ተከፈተ፡፡ ደቅ ደቅደቅ…
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
"አባዬ ምንድነው?
"በሹክሹክታ ጠየቀችኝ
"እኔ እንጃ ..የውጭ በራፍ እየተንኳኳ ነው" ብዬ የተኛሁበትን አልጋ ለቅቄ ወረድኩ፡
‹‹ምነው ልትሄድ ነው እንዴ?"
"አይ ልነሳና ሁኔታውን እንይ"
"ምንድነው?
ማነው?"የእቴቴ ድምፅ ይሰማል
"ቀስ በይ.. ጫማ አላደረግሺም"እህቴ ነች
በዚህ ጊዜ ልጄ"አባዬ" አለችኝ በሹክሹክታ
"ወዬ ማሬ "በተመሳሳይ ቶን
"የውጩን በራፍ ሊከፍቱ ሲወጡ መስኮቱን ክፍት ሆኖ ያዩታል...ለምን ተከፈተ ብለው ወደእዚህ እንዳይመጡ ፈራሁ"
በበሳል አዕምሮዋ ተደምሜ ወደራሴ ሳብኩና ግንባሯን በመሳም ፈጠን ብዬ ወደ
መስኮቱ በመሄድ ዘጋሁት.፡፡አውልቄ ጠረጰዛ ላይ አስቀምጬ የነበረውን ጃኬቴን ለበስኩ ፡፡ጫማዬን አጠለቅኩ..፡፡መነፅሬን ግንባሬ ላይ ሰካሁና ዝግጅ ሆኜ ወንበሩ ላይ በተጠንቀቅ ቁጭ አልኩ።
እቴቴና እህቴ በራፍ ከፍተው ሲወጡ ሰማን ...ልጄ ከመኝታዋ ወረደችና ወደእኔ መጣች፡፡ ስሬ ቆመች ፡፡በቀልጣፍ የአስተሳስብ ብቃቷ ታላቄ ብትሆንም ያው በእድሜ ልጄ ነችና አነሳሁና ታፍዬ ላይ አስቀምጬ ወደ ውስጤ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት ፡አንገቴ ስር ሽጉጥ አለች
..."ማን ነው?"
"እኔ ነኝ ክፈቱ"የሚል የደበዘዘ አይነት የቃላት ልውውጥ ይሰማል"አሁን በዚህ ድንገተኛ ግርግር ምክንያት ሲኦል ከመግባት በላይ በምፈራት በአክስቴ ፊት እቆም ይሆን..?.አረ ፈጣሪ ምንም ሀጢያተኛና ዳተኛ ሰው ብሆንም ይሄን ያህልማ ጨክነህ አሳልፈህ አትሰጠኝም" ስል ፀለይኩ...ፀሎቴን ተከትሎ ‹‹ጉድ ጉድ …››እያለች አክስቴ ወደቤት ስትመለስ ሰማሁ
..‹‹.በቃ መርዶ ነው›››ስል አሰብኩ ..የታላቅ እህቴ ልጅ ምን ሆነው ይሆን?"ከአሁን አሁን ቤቱ በለቅሶ ይደበላለቃል ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ...አሁን ደግሞ ከእኔ መጋለጥ በላይ ለቀናት ስታስበውና ስትዘጋጅበት የከረመችው የልጄ ፕሮግራም መሰነካከሉን ሳስብ ልቤ ላይ ህመም ፈጠረብኝ።
"አባዬ ምንድነው? ጨነቀኝ?"
"አይዞሽ ልጄ.. አይዞሽ"እኔ እራሴም ውስጤ በፍራቻ እየራደ ቢሆንም እሷን ግን ላበረታት ሞከርኩ፡፡
"በጊዜ አንድ ወይም ሁለት ሰዓት እኮ ነበር የምንገባው.. ሸኖን እንዳለፍን መኪናዋ ተበላሸችብን....መከራ አይተን ከሸኖ መካኒክ መቶ ነው ያስነሳት....››
በስመአብ እየቃዠሁ ነው እንዴ? ይሄንን ድምፅ አውቀዋለሁ፡፡
"እንደምትመጪ እኮ አልነገርሺንም...አዲስ አበባ ከገባሽ በኃላ እንኳን አትደውይም እንዴ..?›.
"በእኔ ቤትማ ሰርፐራይዝ ላደርጋችሁ ነበር....ግባ ….አዎ ሻንጣው እዛው ጋ ይሁን..ሌላው መኪናው ላይ ይደር …ነገ ይወርዳል..ተቀመጥ ..አዎ ሶፋው ላይ ተቀመጥ››
"አባዬ. …እማዬ መጣች መሰለኝ"ልጄ ነች ጥርጣሬዋን በጆሮዬ ሹክ ያለችኝ
"አዎ መሰለኝ"
እቅፍ አድርጋ ሳም አደረገችኝ ...እሷ ደስ ስላላት ደስ አለኝ...አረ በራሴም ደስ ብሎኛል ልቤ በውስጤ ስትንፈራፈር ሁሉ ይታወቀኛል።
አሁንም ጆሮዬ እዛኛው ክፍል ነው፡፡..."እማዬ ዛሬ እንኳን አታናግረኝም?"
"ተያት ... ደንግጣ ነው…እንኳን እሷ እኔ እራሱ በድንጋጤ ደርቄልሻለሁ"
"ታዲያ አሁን የት ሄደች ...?"
"ክፍሏ ገብታለች መሠለኝ"
"እሺ ልጄስ....?"
‹‹ተኝታለቻ..."
"ንፍቅ ብላኛለች ..በናትሽ ልቀስቅሳት"
"አይ ..ነገ ዝግጅቷ ላይ ከምትንገላጀጅ ይቅርብሽ..እንደውም በጥዋት ስትነሳ ሰርፐራይዝ ታደርጊያታለሽ"
"ጥሩ ነው… እንደውም እንደዛ ይሻላል።"
ተንፈስ አልኩ...ወደእኛ አይመጡም ማለት ነው፡
"እማ አሁን እናትሽን ልታገኚያት ትፈልጊያለሽ?››ፈራ ተባ እያልኩ ታፋዬ ላይ የተቀመጠችውን ልጄን ጠየቅኳት፡፡
"አይ አሁን ምፈልገው ከአንተ ጋር ተመልሶ መተኛት ነው..ከእሷ ጋር ነገ እተኛለሁ"
እቅፍ አደረኩና ወደአልጋው ይዤት ሄድኩ፤ ጫማዬን አወለቅኩና እቅፍ እንዳደረኳት ተኛሁ...ጆሮዬ ግን እዛው ሳሎን ነው ያለው፡፡
"የሚበላ ነገር ትፈልጋላችሁ ላሙቅ"እህቴ ነች እንግዶቹን የጠየቀችው
"አረ መንገድ ላይ ጂውስና ብስኩት ተጠቅመናል...አሁን መተኛት ነው የምንፈልገው...ለሀሰኖ የእንግዳ ክፍሉን ታሳይዋለሽ ..?እኔ ያው ካንቺ ጋር ነው ምተኛው?
"ምን ጥያቄ አለው...ወንድም ተነስ መኝታህን ላሳይህ››
‹እሺ›
የእግር ኮቴ .ከዛ ረዘም ያለ ዝምታ..ቀጥሎ ማንኳኳት ተሰማኝ
‹‹እቴቴ..እማ.እማዬ››
‹‹አረ አናግሪኝ..ውቅያኖስ አቆርጩ የመጣሁት እኮ አንድም አንቺ ስለናፈቅሺኝ ነው..በአመታት ርዝመት እንኳን ይቅር አትይኝም››
‹‹እማ እንዳልተኛሽ አውቃለሁ›
‹‹እንዴ ምን እየሰራሽ ነው.››እህቴ ነች እንግዳውን አስተኝታ ስትመጣ ያየችው ነገር በመቃወም የተናገረችው፡
‹‹ብታናግረኘ እኮ ብዬ ነው››
‹‹ታገሺ….ነው ወይስ ዛሬውኑ ተመልሰሽ ሀጄ ነሽ››
‹‹ከገዛ እናት ጋር መዘጋጋት እንዴት እንደሚጨንቅ እኮ ስለማታውቂ ነው..›
‹በይ በይ አሁን ወደመኝታችን እንሂድ››
ፀጥታ ሰፈነ…
…….በነጋታው
ከትምህርት ቤቱ ቅፅር ግቢ የፊት ለፊት በራፍ ራቅ ብዬ በአንደኛው መንገድ ቆሜያለሁ።በተቻለኝ መጠን አለባበሴ በቀላሉ ማንነቴን ለመለየት የማያስችል እንዲሆን የተቻለኝን ጥንቃቄ አድርጌያለሁ።በአንድ እጄ ከጄኔራሏ የተዋስኩትን ካሜራ ይዣለሁ ሌላ እጄ ዝም ብሎ ከወዲህ ወዲያ እየተወናጨፈ ግራ መጋባቴን ለተመልካቹ እያሳበቀብኝ ነው። ተማሪዎች ለብቻቸውም ከወላጆቻቸው ጋርም በመሆን ወደውስጥ መግባት ከጀመሩ ደቂቃዎች አልፈዋል። እዛው ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ ከፊት ለፊቴ ካለው መንገድ ሙሉ ቤተሠቤ ሲመጡ ተመለከትኩ።ፈጠን ብዬ ከመሀል መንገድ በመውጣት ደር ላይ የሚገኝ የት/ቤቱ ቢልቦርድን ተከልዬ እይታዬን ወደእነሱ አስተካከልኩ።
ቀድሞ በእይታዬ የገባችው ደርባባዎ እመቤት አክስቴ ነች።ቅሬታ ያረበበት የደግነት ተምሳሌት መሆኑ የሚያስታውቅ የእናት ፊት ...ሮጠህ ሄደህ እግሯ ስር እዛ አቧራው ላይ በመንከባለል ይቅርታ ጠይቃት የሚል ስሜት ከጀርባዬ ወደ ፊት ሲገፈትረኝ ይታወቀኛል።እራሴን በመቆጣጠር ችሎታዬ ላይ ጥርጣሬ ስለገባኝ የተከለልኩበትን የቢልባርድ ብረት ጨምድጄ ያዝኩ።ከመዋረዴ በፊት ትኩረቴን እንደምንም ከእቴቴ አንስቼ ወደ ልጄ አሸጋገርኩት።ልጄ ትንሽ ልዕልት መስላለች..ቦፍ ብሎ ሜዳውን የሞላ ነጭ ቀሚስ ከነጭ ጫማ ጋር ለብሳለች...ያ ክብ ፊቷ የደስታ ብርሀን እየረጨ ነው።በአጠቃላይ ድምቀትና ውበት የተዋሀደባት ሙሉ ጨረቃ መስላለች።አዎ ከአመታት የናፍቆት መቃተት በኃላ በአንድ ቀን እናትንና አባትን ማግኘት ከዚህ በላይም ቢያስፈነድቅ የሚገርም አይሆንም።የእኔ ልጅ የእኔ መላአክ እንኳንም ፈካሽልኝ።
ቀጥሎ እናትዬውን ነው ያየሁት፤ሩቾ ፍፅም ተቀይራ ሌላ ሰው መስላላለች ።በሳቋ ነው የለየኋት።ሙሉ ቆዳዋን አስገፍፋ በሌላ እንደተካች አይነት ነው የተሠማኝ።ደግሞ እንዲህ እረጅም ነበረች እንዴ?እርግጠኛ ነኝ ይሄንን እጄን እንደጥንቱ ፊቷ ላይ አሳርፌ ፊቷን ብዳብስ ይሸረካክታታል...ጉንጮቻ እኮ ተንጠልጥለዋል"ተአምርን በቀኝ እጆ ሌላ አነስ ያለ ወንድ ልጅ በግራ እጇ ይዛ ጠብ እርግፍ ትላለ…ወንድ ልጅ የማነው ልጅ?"
"ውይ ለካ ሁለት ልጆቾ ነው ያሏት….አሁን እቺ ምኗ ነው የሁለት ልጅ እናት የሚመስለው፤ . .ይልቅስ እኔ ነኝ በመጎሳቆሌ የተነሳ ግርጅፍጅፍ ብዬ የአራት ልጆች አባት የምመስለው።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
"አባዬ ምንድነው?
"በሹክሹክታ ጠየቀችኝ
"እኔ እንጃ ..የውጭ በራፍ እየተንኳኳ ነው" ብዬ የተኛሁበትን አልጋ ለቅቄ ወረድኩ፡
‹‹ምነው ልትሄድ ነው እንዴ?"
"አይ ልነሳና ሁኔታውን እንይ"
"ምንድነው?
ማነው?"የእቴቴ ድምፅ ይሰማል
"ቀስ በይ.. ጫማ አላደረግሺም"እህቴ ነች
በዚህ ጊዜ ልጄ"አባዬ" አለችኝ በሹክሹክታ
"ወዬ ማሬ "በተመሳሳይ ቶን
"የውጩን በራፍ ሊከፍቱ ሲወጡ መስኮቱን ክፍት ሆኖ ያዩታል...ለምን ተከፈተ ብለው ወደእዚህ እንዳይመጡ ፈራሁ"
በበሳል አዕምሮዋ ተደምሜ ወደራሴ ሳብኩና ግንባሯን በመሳም ፈጠን ብዬ ወደ
መስኮቱ በመሄድ ዘጋሁት.፡፡አውልቄ ጠረጰዛ ላይ አስቀምጬ የነበረውን ጃኬቴን ለበስኩ ፡፡ጫማዬን አጠለቅኩ..፡፡መነፅሬን ግንባሬ ላይ ሰካሁና ዝግጅ ሆኜ ወንበሩ ላይ በተጠንቀቅ ቁጭ አልኩ።
እቴቴና እህቴ በራፍ ከፍተው ሲወጡ ሰማን ...ልጄ ከመኝታዋ ወረደችና ወደእኔ መጣች፡፡ ስሬ ቆመች ፡፡በቀልጣፍ የአስተሳስብ ብቃቷ ታላቄ ብትሆንም ያው በእድሜ ልጄ ነችና አነሳሁና ታፍዬ ላይ አስቀምጬ ወደ ውስጤ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት ፡አንገቴ ስር ሽጉጥ አለች
..."ማን ነው?"
"እኔ ነኝ ክፈቱ"የሚል የደበዘዘ አይነት የቃላት ልውውጥ ይሰማል"አሁን በዚህ ድንገተኛ ግርግር ምክንያት ሲኦል ከመግባት በላይ በምፈራት በአክስቴ ፊት እቆም ይሆን..?.አረ ፈጣሪ ምንም ሀጢያተኛና ዳተኛ ሰው ብሆንም ይሄን ያህልማ ጨክነህ አሳልፈህ አትሰጠኝም" ስል ፀለይኩ...ፀሎቴን ተከትሎ ‹‹ጉድ ጉድ …››እያለች አክስቴ ወደቤት ስትመለስ ሰማሁ
..‹‹.በቃ መርዶ ነው›››ስል አሰብኩ ..የታላቅ እህቴ ልጅ ምን ሆነው ይሆን?"ከአሁን አሁን ቤቱ በለቅሶ ይደበላለቃል ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ...አሁን ደግሞ ከእኔ መጋለጥ በላይ ለቀናት ስታስበውና ስትዘጋጅበት የከረመችው የልጄ ፕሮግራም መሰነካከሉን ሳስብ ልቤ ላይ ህመም ፈጠረብኝ።
"አባዬ ምንድነው? ጨነቀኝ?"
"አይዞሽ ልጄ.. አይዞሽ"እኔ እራሴም ውስጤ በፍራቻ እየራደ ቢሆንም እሷን ግን ላበረታት ሞከርኩ፡፡
"በጊዜ አንድ ወይም ሁለት ሰዓት እኮ ነበር የምንገባው.. ሸኖን እንዳለፍን መኪናዋ ተበላሸችብን....መከራ አይተን ከሸኖ መካኒክ መቶ ነው ያስነሳት....››
በስመአብ እየቃዠሁ ነው እንዴ? ይሄንን ድምፅ አውቀዋለሁ፡፡
"እንደምትመጪ እኮ አልነገርሺንም...አዲስ አበባ ከገባሽ በኃላ እንኳን አትደውይም እንዴ..?›.
"በእኔ ቤትማ ሰርፐራይዝ ላደርጋችሁ ነበር....ግባ ….አዎ ሻንጣው እዛው ጋ ይሁን..ሌላው መኪናው ላይ ይደር …ነገ ይወርዳል..ተቀመጥ ..አዎ ሶፋው ላይ ተቀመጥ››
"አባዬ. …እማዬ መጣች መሰለኝ"ልጄ ነች ጥርጣሬዋን በጆሮዬ ሹክ ያለችኝ
"አዎ መሰለኝ"
እቅፍ አድርጋ ሳም አደረገችኝ ...እሷ ደስ ስላላት ደስ አለኝ...አረ በራሴም ደስ ብሎኛል ልቤ በውስጤ ስትንፈራፈር ሁሉ ይታወቀኛል።
አሁንም ጆሮዬ እዛኛው ክፍል ነው፡፡..."እማዬ ዛሬ እንኳን አታናግረኝም?"
"ተያት ... ደንግጣ ነው…እንኳን እሷ እኔ እራሱ በድንጋጤ ደርቄልሻለሁ"
"ታዲያ አሁን የት ሄደች ...?"
"ክፍሏ ገብታለች መሠለኝ"
"እሺ ልጄስ....?"
‹‹ተኝታለቻ..."
"ንፍቅ ብላኛለች ..በናትሽ ልቀስቅሳት"
"አይ ..ነገ ዝግጅቷ ላይ ከምትንገላጀጅ ይቅርብሽ..እንደውም በጥዋት ስትነሳ ሰርፐራይዝ ታደርጊያታለሽ"
"ጥሩ ነው… እንደውም እንደዛ ይሻላል።"
ተንፈስ አልኩ...ወደእኛ አይመጡም ማለት ነው፡
"እማ አሁን እናትሽን ልታገኚያት ትፈልጊያለሽ?››ፈራ ተባ እያልኩ ታፋዬ ላይ የተቀመጠችውን ልጄን ጠየቅኳት፡፡
"አይ አሁን ምፈልገው ከአንተ ጋር ተመልሶ መተኛት ነው..ከእሷ ጋር ነገ እተኛለሁ"
እቅፍ አደረኩና ወደአልጋው ይዤት ሄድኩ፤ ጫማዬን አወለቅኩና እቅፍ እንዳደረኳት ተኛሁ...ጆሮዬ ግን እዛው ሳሎን ነው ያለው፡፡
"የሚበላ ነገር ትፈልጋላችሁ ላሙቅ"እህቴ ነች እንግዶቹን የጠየቀችው
"አረ መንገድ ላይ ጂውስና ብስኩት ተጠቅመናል...አሁን መተኛት ነው የምንፈልገው...ለሀሰኖ የእንግዳ ክፍሉን ታሳይዋለሽ ..?እኔ ያው ካንቺ ጋር ነው ምተኛው?
"ምን ጥያቄ አለው...ወንድም ተነስ መኝታህን ላሳይህ››
‹እሺ›
የእግር ኮቴ .ከዛ ረዘም ያለ ዝምታ..ቀጥሎ ማንኳኳት ተሰማኝ
‹‹እቴቴ..እማ.እማዬ››
‹‹አረ አናግሪኝ..ውቅያኖስ አቆርጩ የመጣሁት እኮ አንድም አንቺ ስለናፈቅሺኝ ነው..በአመታት ርዝመት እንኳን ይቅር አትይኝም››
‹‹እማ እንዳልተኛሽ አውቃለሁ›
‹‹እንዴ ምን እየሰራሽ ነው.››እህቴ ነች እንግዳውን አስተኝታ ስትመጣ ያየችው ነገር በመቃወም የተናገረችው፡
‹‹ብታናግረኘ እኮ ብዬ ነው››
‹‹ታገሺ….ነው ወይስ ዛሬውኑ ተመልሰሽ ሀጄ ነሽ››
‹‹ከገዛ እናት ጋር መዘጋጋት እንዴት እንደሚጨንቅ እኮ ስለማታውቂ ነው..›
‹በይ በይ አሁን ወደመኝታችን እንሂድ››
ፀጥታ ሰፈነ…
…….በነጋታው
ከትምህርት ቤቱ ቅፅር ግቢ የፊት ለፊት በራፍ ራቅ ብዬ በአንደኛው መንገድ ቆሜያለሁ።በተቻለኝ መጠን አለባበሴ በቀላሉ ማንነቴን ለመለየት የማያስችል እንዲሆን የተቻለኝን ጥንቃቄ አድርጌያለሁ።በአንድ እጄ ከጄኔራሏ የተዋስኩትን ካሜራ ይዣለሁ ሌላ እጄ ዝም ብሎ ከወዲህ ወዲያ እየተወናጨፈ ግራ መጋባቴን ለተመልካቹ እያሳበቀብኝ ነው። ተማሪዎች ለብቻቸውም ከወላጆቻቸው ጋርም በመሆን ወደውስጥ መግባት ከጀመሩ ደቂቃዎች አልፈዋል። እዛው ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ ከፊት ለፊቴ ካለው መንገድ ሙሉ ቤተሠቤ ሲመጡ ተመለከትኩ።ፈጠን ብዬ ከመሀል መንገድ በመውጣት ደር ላይ የሚገኝ የት/ቤቱ ቢልቦርድን ተከልዬ እይታዬን ወደእነሱ አስተካከልኩ።
ቀድሞ በእይታዬ የገባችው ደርባባዎ እመቤት አክስቴ ነች።ቅሬታ ያረበበት የደግነት ተምሳሌት መሆኑ የሚያስታውቅ የእናት ፊት ...ሮጠህ ሄደህ እግሯ ስር እዛ አቧራው ላይ በመንከባለል ይቅርታ ጠይቃት የሚል ስሜት ከጀርባዬ ወደ ፊት ሲገፈትረኝ ይታወቀኛል።እራሴን በመቆጣጠር ችሎታዬ ላይ ጥርጣሬ ስለገባኝ የተከለልኩበትን የቢልባርድ ብረት ጨምድጄ ያዝኩ።ከመዋረዴ በፊት ትኩረቴን እንደምንም ከእቴቴ አንስቼ ወደ ልጄ አሸጋገርኩት።ልጄ ትንሽ ልዕልት መስላለች..ቦፍ ብሎ ሜዳውን የሞላ ነጭ ቀሚስ ከነጭ ጫማ ጋር ለብሳለች...ያ ክብ ፊቷ የደስታ ብርሀን እየረጨ ነው።በአጠቃላይ ድምቀትና ውበት የተዋሀደባት ሙሉ ጨረቃ መስላለች።አዎ ከአመታት የናፍቆት መቃተት በኃላ በአንድ ቀን እናትንና አባትን ማግኘት ከዚህ በላይም ቢያስፈነድቅ የሚገርም አይሆንም።የእኔ ልጅ የእኔ መላአክ እንኳንም ፈካሽልኝ።
ቀጥሎ እናትዬውን ነው ያየሁት፤ሩቾ ፍፅም ተቀይራ ሌላ ሰው መስላላለች ።በሳቋ ነው የለየኋት።ሙሉ ቆዳዋን አስገፍፋ በሌላ እንደተካች አይነት ነው የተሠማኝ።ደግሞ እንዲህ እረጅም ነበረች እንዴ?እርግጠኛ ነኝ ይሄንን እጄን እንደጥንቱ ፊቷ ላይ አሳርፌ ፊቷን ብዳብስ ይሸረካክታታል...ጉንጮቻ እኮ ተንጠልጥለዋል"ተአምርን በቀኝ እጆ ሌላ አነስ ያለ ወንድ ልጅ በግራ እጇ ይዛ ጠብ እርግፍ ትላለ…ወንድ ልጅ የማነው ልጅ?"
"ውይ ለካ ሁለት ልጆቾ ነው ያሏት….አሁን እቺ ምኗ ነው የሁለት ልጅ እናት የሚመስለው፤ . .ይልቅስ እኔ ነኝ በመጎሳቆሌ የተነሳ ግርጅፍጅፍ ብዬ የአራት ልጆች አባት የምመስለው።
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹ በቅርቡ ልታየው አይደል ››በማለት ድፍን ያለ መልስ መለስችለትና ተያይዘን ወጡ ...
‹‹እሺ ቦታ ትመርጣላችሁ ወይስ እኔ ልምረጥ?››መድህኔ ነው ወደ መኪና ከመግባታቸው በፊት የጠየቀው፡፡
"ቦታውን አንተ ምረጥ ..ግን ጭፈራ ቤት መሆን አለበት"አለችው ልዩ፡
"አሪፍ ነዋ"አለ ፊቱ በርቶ..ከዛ ወደ መኪናው መራመድ ጀመረ...ተከተሉኝ፡፡
እስከ ለሊቱ ሰባት ሰዓት ቀወጡት ..በዋነኝነት ተዋናዬቹ ሶስቱ ነበሩ፡፡ ከመሀከላቸው ቃል መጠጥ አይጠጣም .... ውሀ ይዞ እነሱን መከታተል ነበር ዋና ስራው፡፡ሲጨፍሩ ያየቸዋል... ሲንገዳገዱ ይደግፋቸዋል... ፡፡ እነሱም በእሱ ተማምነን ዘና ብለን እየቀወጡ ነው ምሽቱን በፈንጠዝያ ያሳለፉት።ለነገሩ ልዩም በአብዛኛው ከእሱ ተለጥፋ ነው ያመሸችው፡፡
‹‹ሚስትህ ባሌን እኳ አንሳፋፈችው››አለችው፡፡
‹‹ምነው ቀናሽ እንዴ?››
‹‹ለምን አልቀና እኔ እንደአንተ ደመበራድ አይደለሁም››
እና ምን ይሻላል
‹‹ያው ምን ይሻላል .መጨረሻቸውን ማለት ነው››
እስከወዲያኛው ብትቀማሽስ››
ትሞክረዋ›
<<ምን ታደርጊያለሽ››
እሾክን በሾክ ነዋ…እሷ እኮ ባል አላት›› አለችው…ፉከራዋ አሳቀው፡፡
መድህኔና ጊፍቲ ስለእነሱ ሹክሹክታ ደንታም ሳይሰጣቸው በጭፈራቸው ተመስጠዋል፡፡ ሁለቱም አደገኛ ጨፋሪዎች ናቸው ...ደግሞ በሚገርም ጥምረት ተግባብተው በአየር ላይ የመብረር ያህል አቅላቸውን ስተው ተጣብቀው ሲደንሱ ላያቸወ ከአየን ያውጣችው ያስብላሉ ፡፡ አሁን እዚህ ጭፈራ ቤት ያሉ ሁሉ ልዩና ቃልን ቀዝቃዛ ፍቅረኞች ….ጊፍቲና መድህኔ ደግሞ የበለጡ የሚያምሩና የሚግባብ የጋለ ፍቅር ላይ ያሉ ጥንዶች እንደሆኑ ምሎ ሊናገር ይችላል። ‹‹ግን በትክክልም መሆን ያለበት እንደዚህ ነው።አዎ መድህኔ እኮ በጣም ቆንጆ ፤ዘናጭ፤ ሀብታምና ጥሩ ስነምግባር ያለው ሰው ነው...እና ጊፍቲ መድህኔ ፍቅረኛዋ ቢሆን በጣም ጥሩና የተመቸ ኑሮ ትኖራለች...አዎ እሱን ብታገኝ በጣም እድለኛ ነች።›ስትል አብሰለሰልች፡፡
ግን መድህኔ እንደምትይው ሁሉን የሚያሟላ ተመራጭ ወንድ ከሆነ አንቺስ ለምን እሱን ለቀሽ ቃልን ተመኘሽ?ብሎ የሚጠይቃት ሰው ካለ ምን አይነት መልስ ልትመልስ እንደምትችል አታውቅም..
.ስለቃል የሚሰማት ስሜት ጥልቅና መንፈሳዊ ነው"..ልክ የመድህኔን ኳሊቲ በቀላሉ ዘርዝራ እንደተናገረችው የቃልን እንደዛ ማድረግ አትችልም...እና ደግሞ የቃልን ጉዳይ ባይሆንባት በማንም ሌላ ወንድ መድህኔን መቀየር አትፈልግም ነበር...እና ደግሞ ማንም ሌላ ሴት መድህኔን ልትቀማት ሞክራ ቢሆን ኖሮ አንገቷን ቀንጥሳ ነበር የምትጥላት።ስለ ቃል ሚሰማት ስሜት ይሄን ያህል ውስብስብ ነው
ሰባት ሰዓት ስላለፈ እዛው ሲጨፍሩበት ካመሹበት ሆቴል አንድ ባለ ሁለት አላጋ ክፍል ተያዘና እየተጓተቱ ሄድን ፡፡እውነት ለመናገር ብክት እስኪሉ ሰክረዋል.... መኝታ ቤት እንደገቡ ብርድ ልብስ ገልጦ ከውስጥ የገባ የለም...ልዩና መድህኔ አንድ አልጋ ላይ ቃልና ጊፍቲ አንድ ላይ ተመሳቅለው ተኙ። ልዩ ከጎኖ እጮኛዋን መድህኔ ሰውነቷ ላይ ተለጠፋ የተኛች ቢሆንም ነፍሷ ግን ቃል እቅፍ ውስጥ ነበር ተሸጉጣ ያደረችው።
///
ጥዋት አንድ ሰዓት ተኩል ሲል ከአንቅልፋቸው ተነስተው ሁሉም ለብሰው ያደሩትን የተጨማዳደ ልበሳቸውን በተቻለ መጠን አስተካከሉና ወደሬስቶራንት ጎራ ብለው ፤አፒታይታቸው በፈቀደላቸው መጠን ቁርስ በልተው በማጠናቅ ሆቴሉን ለቀው ለመውጣት ዝግጁ ሆኑ ከዛ ልዩ ጊፍቲን ቢሮዋ ድረሰ ሸኝታት ወደትምህርት ቤት እንድትሄድ በተመሳሳይ ደግሞ መድህኔ ቃልን መስሪያ ቤቱ ድረስ አድርሶት ወደስራው ሊሄድ ድልድል አወጡ፡፡ልዩ እንዲሆን የፈለገችው ተቃራኒውን ነበር...እሷ ቃልን እንድትሸኘው መድህኔ ደግሞ ይህቺን መዥገር ነገር እንዲያደርሳት… በዛውም ሁለቱ ስለማታው የሰመረ የዳንስ ጥምረታቸው እያወሩና ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ እንዲሄዱ ፈልጋ ነበር ….ግን እንዴት ብላ ተቃውሞ ታቅርብ …?ሳትወድ በግድ በድልድሉ ተስማማችና ደስተኛ እንደሆነች ለማስመሰል እየጣረች ጊፍቲን አሳፍራ ወደቢሮዋ ጉዞ ጀመረች…ለረጂም ደቂቃ ምንም አልተነጋገሩም…..ጊፍቲ ነበረች ከዝምታዋ ያነቃቻኝ፡፡
‹‹ምነው እኔን ጥለሽ ጭልጥ አልሽ .?››
ድንገት አፏ ላይ የመጣላትን መልስ መለሰችላት‹‹ስለማታው አስደሳች ምሽት እያሰብኩ ነበር› …እንደዛ ያለችው. እውነት ስላለችው ነገር እያሰበችበት ስለነበር ሳይሆን ሰለማታው ቆይታቸው ምን እንደተሰማት ለመገምገም እንዲረዳት ነው፡፡
‹‹ውይ ብታይ እኔም በጣም ደስ ብሎኛል...እንዲህ አይነት ፍንጥዝጥዝ ያለ ምሽት ካሳልፍኩ ረጂም ጊዜ ሆኖኝ ነበር.በጣም አመሰግናለሁ›› አለች ጊፍቲ…
ልዩም‹‹አሀ አንዳሰብኩት በጣም ደስተኛ ነበረች ማለት ነው?››ስትል በውስጧ አሰበቸና ይበልጥ ዝርዝሩን ለመረዳት ንግግሯን ቀጠለች ‹‹ደግሞ በጣም ደናሽ ነሽ›ስትል የአድናቆት ቃል ሰነዘረች፡፡
‹‹አዎ ዳንስና ጭፈራ በጣም ወዳለሁ..ግን ባልሽን ጫፍ ላይ አልደርስም…በስመአብ አጥንት ያለው እኮ አይመስልም››
ጊፍቲ በአንድ ቀን ቆይታ ለመድሀኔ ያደረባት አድናቆቶ ካሰበችው በላይ የተጋነነ ሆኖ ነው ያገኘችው…እርግጥ መድሀኔ ሁሉም የሚያወራለት ጨፋሪ እንደሆነ እራሷም ልዩ ታውቃለች…ጊፍቲ በምታወራለት ልክ ግን ሌላ ሰው ሲያደንቀው ሰምታ አታውቅም..እሷ ያው እንደቃል የቀዘቀዘች ባትሆንም ለጭፈራ ያን ያህል ስለሆነች በእሷ ልክ የመድሀኔን ችሎታ ባይታያት አይፈረድባትም፡ስለዚህ ይሄ መደነቋ ሳይበርድ ልትጠቀምበት ይገባል ብላ አሰበች…በጣም ፈጣን የሆነ እቅድ በእምሮዋ ተሰነቀረ፡፡
‹‹ውይ ይቅርታ…አንድ ነገር እያሰብኩ ነበር…ከመድህኔ ጋር ሳምንት ኩሪፍቱ ለመሄድ ቀጠሮ ነበረን፤ በእኛ እስፖንሰርነት ለምን አንቺና ቃል አትቀላቀሉንም››
ከተማ ወጥቶ የመዝናናት ምንም አይነት ዕቅድ የላቸውም ….ግን እሷ ከተስማማች መድህኔን ከከተማ ወጥቶ መዝናናት እንደምትፈልግ መናገር ብቻ ነው የሚጠበቅባት….ምንም አይነት ወሳኝ የስራ ቃጠሮ ይኑረው ወይም ሌላ ፕሮግራም ሁሉንም ጣጥሎ ፍላጎቷን እንደሚያሞላላት እርግጠኛ ነች…ለዛ ነው በልቧ ሙሉነት የግብዣውን ሀሳብ ያቀረበችላት፡፡
‹‹ወይ በጣም ደስ ይለኝ ነበር…?ግን ቃል የሚመቸው አይመስለኝም….መስሪያ ቤቱ ለአምስት ቀን ፊልድ ክፍለሀገር ሊለከው ነው…ነገ ክፍለሀገር ይሄዳል..››አለቻት፡፡
ልዩ በጊፍቲ መልስ ደስ አለት ፡፡ደስ ያለት ለአምስት ቀን ሙሉ ቃልን ላታየው ባለመቻሏ አይደለም…ግን በጉዞችን የቃል አለመኖር ጥሩ ሆኖ ነው ያገኘችሁት… ጊፍቲን ከመድህኔ ጋር ይበልጥ እንዲቀራረብ ለማድረግ አሪፍ እድል ይሆናል ብላ ስላሰበች ነው፡፡
‹‹ታዲያ ለምን አንቺ አትቀላቀይንም ?..በሌላ ዙር ደግሞ ቃልን ጨምረን ተሟልተን እንሄዳለን››
‹‹ተይ ባክሽ..ብቻችሁን ብታሳልፉ ይሻላል?፡፡››መግደርደር መሆኑን በደንብ በሚያሳብቅ ፈራ ተባ ባለ ንግግር መለሰችላት፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹ በቅርቡ ልታየው አይደል ››በማለት ድፍን ያለ መልስ መለስችለትና ተያይዘን ወጡ ...
‹‹እሺ ቦታ ትመርጣላችሁ ወይስ እኔ ልምረጥ?››መድህኔ ነው ወደ መኪና ከመግባታቸው በፊት የጠየቀው፡፡
"ቦታውን አንተ ምረጥ ..ግን ጭፈራ ቤት መሆን አለበት"አለችው ልዩ፡
"አሪፍ ነዋ"አለ ፊቱ በርቶ..ከዛ ወደ መኪናው መራመድ ጀመረ...ተከተሉኝ፡፡
እስከ ለሊቱ ሰባት ሰዓት ቀወጡት ..በዋነኝነት ተዋናዬቹ ሶስቱ ነበሩ፡፡ ከመሀከላቸው ቃል መጠጥ አይጠጣም .... ውሀ ይዞ እነሱን መከታተል ነበር ዋና ስራው፡፡ሲጨፍሩ ያየቸዋል... ሲንገዳገዱ ይደግፋቸዋል... ፡፡ እነሱም በእሱ ተማምነን ዘና ብለን እየቀወጡ ነው ምሽቱን በፈንጠዝያ ያሳለፉት።ለነገሩ ልዩም በአብዛኛው ከእሱ ተለጥፋ ነው ያመሸችው፡፡
‹‹ሚስትህ ባሌን እኳ አንሳፋፈችው››አለችው፡፡
‹‹ምነው ቀናሽ እንዴ?››
‹‹ለምን አልቀና እኔ እንደአንተ ደመበራድ አይደለሁም››
እና ምን ይሻላል
‹‹ያው ምን ይሻላል .መጨረሻቸውን ማለት ነው››
እስከወዲያኛው ብትቀማሽስ››
ትሞክረዋ›
<<ምን ታደርጊያለሽ››
እሾክን በሾክ ነዋ…እሷ እኮ ባል አላት›› አለችው…ፉከራዋ አሳቀው፡፡
መድህኔና ጊፍቲ ስለእነሱ ሹክሹክታ ደንታም ሳይሰጣቸው በጭፈራቸው ተመስጠዋል፡፡ ሁለቱም አደገኛ ጨፋሪዎች ናቸው ...ደግሞ በሚገርም ጥምረት ተግባብተው በአየር ላይ የመብረር ያህል አቅላቸውን ስተው ተጣብቀው ሲደንሱ ላያቸወ ከአየን ያውጣችው ያስብላሉ ፡፡ አሁን እዚህ ጭፈራ ቤት ያሉ ሁሉ ልዩና ቃልን ቀዝቃዛ ፍቅረኞች ….ጊፍቲና መድህኔ ደግሞ የበለጡ የሚያምሩና የሚግባብ የጋለ ፍቅር ላይ ያሉ ጥንዶች እንደሆኑ ምሎ ሊናገር ይችላል። ‹‹ግን በትክክልም መሆን ያለበት እንደዚህ ነው።አዎ መድህኔ እኮ በጣም ቆንጆ ፤ዘናጭ፤ ሀብታምና ጥሩ ስነምግባር ያለው ሰው ነው...እና ጊፍቲ መድህኔ ፍቅረኛዋ ቢሆን በጣም ጥሩና የተመቸ ኑሮ ትኖራለች...አዎ እሱን ብታገኝ በጣም እድለኛ ነች።›ስትል አብሰለሰልች፡፡
ግን መድህኔ እንደምትይው ሁሉን የሚያሟላ ተመራጭ ወንድ ከሆነ አንቺስ ለምን እሱን ለቀሽ ቃልን ተመኘሽ?ብሎ የሚጠይቃት ሰው ካለ ምን አይነት መልስ ልትመልስ እንደምትችል አታውቅም..
.ስለቃል የሚሰማት ስሜት ጥልቅና መንፈሳዊ ነው"..ልክ የመድህኔን ኳሊቲ በቀላሉ ዘርዝራ እንደተናገረችው የቃልን እንደዛ ማድረግ አትችልም...እና ደግሞ የቃልን ጉዳይ ባይሆንባት በማንም ሌላ ወንድ መድህኔን መቀየር አትፈልግም ነበር...እና ደግሞ ማንም ሌላ ሴት መድህኔን ልትቀማት ሞክራ ቢሆን ኖሮ አንገቷን ቀንጥሳ ነበር የምትጥላት።ስለ ቃል ሚሰማት ስሜት ይሄን ያህል ውስብስብ ነው
ሰባት ሰዓት ስላለፈ እዛው ሲጨፍሩበት ካመሹበት ሆቴል አንድ ባለ ሁለት አላጋ ክፍል ተያዘና እየተጓተቱ ሄድን ፡፡እውነት ለመናገር ብክት እስኪሉ ሰክረዋል.... መኝታ ቤት እንደገቡ ብርድ ልብስ ገልጦ ከውስጥ የገባ የለም...ልዩና መድህኔ አንድ አልጋ ላይ ቃልና ጊፍቲ አንድ ላይ ተመሳቅለው ተኙ። ልዩ ከጎኖ እጮኛዋን መድህኔ ሰውነቷ ላይ ተለጠፋ የተኛች ቢሆንም ነፍሷ ግን ቃል እቅፍ ውስጥ ነበር ተሸጉጣ ያደረችው።
///
ጥዋት አንድ ሰዓት ተኩል ሲል ከአንቅልፋቸው ተነስተው ሁሉም ለብሰው ያደሩትን የተጨማዳደ ልበሳቸውን በተቻለ መጠን አስተካከሉና ወደሬስቶራንት ጎራ ብለው ፤አፒታይታቸው በፈቀደላቸው መጠን ቁርስ በልተው በማጠናቅ ሆቴሉን ለቀው ለመውጣት ዝግጁ ሆኑ ከዛ ልዩ ጊፍቲን ቢሮዋ ድረሰ ሸኝታት ወደትምህርት ቤት እንድትሄድ በተመሳሳይ ደግሞ መድህኔ ቃልን መስሪያ ቤቱ ድረስ አድርሶት ወደስራው ሊሄድ ድልድል አወጡ፡፡ልዩ እንዲሆን የፈለገችው ተቃራኒውን ነበር...እሷ ቃልን እንድትሸኘው መድህኔ ደግሞ ይህቺን መዥገር ነገር እንዲያደርሳት… በዛውም ሁለቱ ስለማታው የሰመረ የዳንስ ጥምረታቸው እያወሩና ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ እንዲሄዱ ፈልጋ ነበር ….ግን እንዴት ብላ ተቃውሞ ታቅርብ …?ሳትወድ በግድ በድልድሉ ተስማማችና ደስተኛ እንደሆነች ለማስመሰል እየጣረች ጊፍቲን አሳፍራ ወደቢሮዋ ጉዞ ጀመረች…ለረጂም ደቂቃ ምንም አልተነጋገሩም…..ጊፍቲ ነበረች ከዝምታዋ ያነቃቻኝ፡፡
‹‹ምነው እኔን ጥለሽ ጭልጥ አልሽ .?››
ድንገት አፏ ላይ የመጣላትን መልስ መለሰችላት‹‹ስለማታው አስደሳች ምሽት እያሰብኩ ነበር› …እንደዛ ያለችው. እውነት ስላለችው ነገር እያሰበችበት ስለነበር ሳይሆን ሰለማታው ቆይታቸው ምን እንደተሰማት ለመገምገም እንዲረዳት ነው፡፡
‹‹ውይ ብታይ እኔም በጣም ደስ ብሎኛል...እንዲህ አይነት ፍንጥዝጥዝ ያለ ምሽት ካሳልፍኩ ረጂም ጊዜ ሆኖኝ ነበር.በጣም አመሰግናለሁ›› አለች ጊፍቲ…
ልዩም‹‹አሀ አንዳሰብኩት በጣም ደስተኛ ነበረች ማለት ነው?››ስትል በውስጧ አሰበቸና ይበልጥ ዝርዝሩን ለመረዳት ንግግሯን ቀጠለች ‹‹ደግሞ በጣም ደናሽ ነሽ›ስትል የአድናቆት ቃል ሰነዘረች፡፡
‹‹አዎ ዳንስና ጭፈራ በጣም ወዳለሁ..ግን ባልሽን ጫፍ ላይ አልደርስም…በስመአብ አጥንት ያለው እኮ አይመስልም››
ጊፍቲ በአንድ ቀን ቆይታ ለመድሀኔ ያደረባት አድናቆቶ ካሰበችው በላይ የተጋነነ ሆኖ ነው ያገኘችው…እርግጥ መድሀኔ ሁሉም የሚያወራለት ጨፋሪ እንደሆነ እራሷም ልዩ ታውቃለች…ጊፍቲ በምታወራለት ልክ ግን ሌላ ሰው ሲያደንቀው ሰምታ አታውቅም..እሷ ያው እንደቃል የቀዘቀዘች ባትሆንም ለጭፈራ ያን ያህል ስለሆነች በእሷ ልክ የመድሀኔን ችሎታ ባይታያት አይፈረድባትም፡ስለዚህ ይሄ መደነቋ ሳይበርድ ልትጠቀምበት ይገባል ብላ አሰበች…በጣም ፈጣን የሆነ እቅድ በእምሮዋ ተሰነቀረ፡፡
‹‹ውይ ይቅርታ…አንድ ነገር እያሰብኩ ነበር…ከመድህኔ ጋር ሳምንት ኩሪፍቱ ለመሄድ ቀጠሮ ነበረን፤ በእኛ እስፖንሰርነት ለምን አንቺና ቃል አትቀላቀሉንም››
ከተማ ወጥቶ የመዝናናት ምንም አይነት ዕቅድ የላቸውም ….ግን እሷ ከተስማማች መድህኔን ከከተማ ወጥቶ መዝናናት እንደምትፈልግ መናገር ብቻ ነው የሚጠበቅባት….ምንም አይነት ወሳኝ የስራ ቃጠሮ ይኑረው ወይም ሌላ ፕሮግራም ሁሉንም ጣጥሎ ፍላጎቷን እንደሚያሞላላት እርግጠኛ ነች…ለዛ ነው በልቧ ሙሉነት የግብዣውን ሀሳብ ያቀረበችላት፡፡
‹‹ወይ በጣም ደስ ይለኝ ነበር…?ግን ቃል የሚመቸው አይመስለኝም….መስሪያ ቤቱ ለአምስት ቀን ፊልድ ክፍለሀገር ሊለከው ነው…ነገ ክፍለሀገር ይሄዳል..››አለቻት፡፡
ልዩ በጊፍቲ መልስ ደስ አለት ፡፡ደስ ያለት ለአምስት ቀን ሙሉ ቃልን ላታየው ባለመቻሏ አይደለም…ግን በጉዞችን የቃል አለመኖር ጥሩ ሆኖ ነው ያገኘችሁት… ጊፍቲን ከመድህኔ ጋር ይበልጥ እንዲቀራረብ ለማድረግ አሪፍ እድል ይሆናል ብላ ስላሰበች ነው፡፡
‹‹ታዲያ ለምን አንቺ አትቀላቀይንም ?..በሌላ ዙር ደግሞ ቃልን ጨምረን ተሟልተን እንሄዳለን››
‹‹ተይ ባክሽ..ብቻችሁን ብታሳልፉ ይሻላል?፡፡››መግደርደር መሆኑን በደንብ በሚያሳብቅ ፈራ ተባ ባለ ንግግር መለሰችላት፡
#ታምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ይሄ ክስት ከተከሰተ ከ5 ዓመት በኃላ 10ኛ ክፍል ማትሪክ ለመፈተን ዝግጅት ላይ እያለች ድንገት እናትዬው በህይወቷ ለሁለተኛ ጊዜ ክፉኛ ታመመች፡፡ አፋፍሰው ደሎ ሆስፒታል አስገቧት….ወደጎባ ወይም ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ትባላለች ብለው ሲጠብቁ ከሶስት ቀን በኃላ ወደቤት መልሳችሁ ውሰዷት የሚል ትዕዛዝ ተሰጣቸው፡፡
ቀጥታ እየተውረገረገች ዶክተሩ ጋ ገባች፡፡
‹‹አቤት ምን ነበር?›
‹‹ስለእናቴ ጉዳይ ነበር››
‹‹ስለእናትሽ ምን?››
ዝልፍልፍ ብላ ደከማለች እኮ ….በህይወትና በሞት መካከል ሆና እየተመለከታችሁ ወደቤት መልሷት ማለት ምን ማለት ነው...?
ካልቻላቸሁ አልቻልንም ብላችሁ ሪፈር ማለት ነው እንጂ ወደቤት መልሷት ማለት ምን ማለት ነው….?ግልፅ አልሆነልኝም፡፡››
‹እስኪ ተረጋጋግተሸ ተቀመጪና ላስረደዳሽ..እንደው ስታስቢው ይሄንን ቀደም ተከተል ማናውቅ አድርገሽ ነው ምታስቢን ?››
‹‹እኔ እንጃ ግራ አጋባችሁኛ››
‹‹ሁኔታውን እኮ ለአያትሽ አስረድቼቸዋለሁ...እሳቸው ቀስ ብለው ያስረዱሻል፡፡››
‹‹እና እናቴ …የእኔ ውዷ እናት …የሌላ አለም ፈጡርን በፍቅር ጠብ ያደረገችው ተአምረኛዋ እናት እንደቀልድ በአንድ ወር ውስጥ ትሞታለች እያላችሁኝ ነው?››
‹‹አይ እኛ አይደለም እንደዛ ያልነው.. እናትሽ ያለባቸው በሽታ ያለበት ደረጃ እና አሁን ባለው የሳይንስ ግኝት በሽታውን ለማከም ያለንን አቅም ከግምት በማስገባት ነው፡፡››
‹‹እና በቃ ውሳኔያችሁ እንደዛ ነው?››
‹‹አዝናለሁ…ለእሳቸውም የመጨረሻዎቹን ቀናቶች ወዲህ ወዲያ እያሉ ውጤት ለማይኖረው ነገር ከሚንገላቱ በቤተሰባቸው እንክብካቤ ውስጥ ሆነው ቢያሳልፉ ይሻላቸዋል፡፡
‹‹እኔ እናቴን ካዳንኳት…ምን ትላለህ?››
‹‹ስለአንቺ የሰማሁትን ለማመን እገደዳለሁ››
‹‹ስለእኔ ምን ሰማህ?››በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹የመላዕክት ዝርያ እንዳለብሽ››
‹‹አይ ያሉህ እንኳን እንደዛ አይደለም…የደቢሎስ ዝርያ አለባት ነው ሊሉህ የሚችሉት፡፡››
‹‹ያው ነው…ዳቢሎስም ሌላ ምንም ሳይሆን መላዐክ ነው…ለዛውም ከዋናዎቹ አንድና ዋነኛው የነበረ.በተወሰነ ያለመግባባት ከእግዚያብር የመኖሪያ ግዛት የተሰደደ…››
‹‹የተናገርከው ከልብህ ስለሆነ አስደስተሀኛል…ለማንኛውም ስለጮህኩብህ ይቅርታ.. እናቴን ወደቤት ወስዳታለሁ...እናም አድናታለሁ።››
‹‹እንግዲህ እንዳልኩሽ ነው….ለማንኛውም እቤት ብቅ እያልኩ አያቸዋለሁ..ድንገተኛ ነገር ተፈጥሮ ከፈለግሺኝም ደውይልኝ› ብሎ ቁጥሩን ሰጣት ተቀበለችውና አመስግናለሁ ብላ ወጣች፡፡
ወዲያው ነበር እናቷን ይዛ ወደቤት የገባችው፡፡ግርግሩ ጋብ ሲል ወደ እናቷ መኝታ ቀረበችና…በቀናቶቸ በሽታ የሰለሉና የደከሙ እጆቾን በእጆቾ ውስጥ አስገብታ እየዳበሰች፡፡
‹‹ሀርሜ አይዞሽ እኔ ምንም እንድትሆኚ አልፈቅድም››
‹‹ልጄ በዚህ ጉዳይ እንድትጨነቂ አልፈልግም…እንደውም መሄድ እፈልጋለሁ።››ስትል መለሰችላት፡፡
እማ ምን ማለት ነው …እኔን ጥለሽ ወደየት ነው የምትሄጂው…አንቺ ከሌለሽ እኮ እኔም መኖር በጣም ነው የሚከብደኝ …ማን ነው የሚረዳኝ?›
‹‹ልጄ አንቺ የአባትሽ ልጅ ነሽ. .በጣም ጠንካራና የማትሰበሪ ነሽ…እኔ ብሄድ ምን አልባት አባትሽን አገኘው ይሆናል፡፡ምን አልባት መልሰን አንድ ላይ የመሆን እድል እናገኝ ይሆናል፡፡
‹አይ እንደዛ አይሆንም…የእሱ አለምና አንቺ ስትሞቺ የምትሄጂበት ቦታ አንድ መሆኑን በምን እርግጠኛ ሆንሽ? እንዲህ አይነት ቁማርማ እንድትጫወቺ አልፈቅድም..በይ አሁን ደክሞሻል.. እረፊ .የሆነ ቦታ ደርሼ መጣሁ…››
‹‹ደግሞ ወዴት ልትሄጂ ነው?››
‹‹እማ ደግሞ የሆነ ቦታ አልኩሽ እኮ›ብላ ግንባሯን በመሳም ወጥታ ሄደች.. ግቢውን እንደለቀቀች ከጀርባዋ ንሰሯ እየተምዘገዘገ መጥቶ ተከሻዋ ላይ አረፈ.እርምጃዋን እልገታችም….በሀሳብ እየተብሰለሰለች ቀጥታ ከተማውን ለቃ ወደ ያዶት ወንዝ ነው የሄደችው…እናትና አባቷ ተገናኝተውበት ወደነበረ ልክ እንደቤተመቅደስ እያየች ወደ አደገችበት ቦታ ነው የሄደችው፡፡እንደደረሰች ንስሯ ከትከሻዋ ለቆ ተነሳና በአካበባቢው ካሉት ብዛት ያላቸው ግዙፉ ዛፎች መካከል አንዱ ላይ አረፈ.እሷም ልብሷን አወላልቃ ዛፉ ላይ እስከግማሽ እየተንጠላጠለችና እየተሳበች ወጣችና አስር ሜትር ከፍታ ላይ ከደረሰች በኃላ ዘላ እየተምዘገዘገች ወንዙ ውስጥ ቦጭረቅ ብላ ገባች…ከዛ ወደውስጥ ሰመጠችና የሆነ ሚስጥራዊ ምርምር እንደሚያካሂድ የባህር ውስጥ አሳሽ ውስጥ ለውስጥ ትንፋሿን ተቆጣጥራ ከወዲህ ወዲያ እየተመላለሰች.፡፡
ግማሽ ለሚሆን ሰዓት ከዋኘች በኃላ የድካም ስሜት ሲሰማት ወጥታ ልብሷን ለበሰች፡፡የመጨናነቅ ስሜቷ አሁን ቀለል ብሏታል…ወደዚህ ቦታ የምትመጠጣው ለመታደስ ነው.ከአባቷ መንፈስ ጋር ለመገናኘት..እሱ የረገጣቸውን የወንዙን ወለል ለመርገጥ ፤እሱ የተነፈሰባቸውን ቦታዎች እሷም ልትተነፍስባቸውና ከእሱ ጋር ያላትን የመንፈስ መስተጋብር ለማጎልበት ነው....እናም ደግሞ ምን አልባት አንድ ቀን ቡልቅ ብሎ ከዚህ ከውሀው መሀል በመውጣት ተጠምጥሞ ይስመኛል…በሚል ድብቅ ምኞትም በመጓጓት ነው እንደዛ የምታደረግው;፡
ለባብሳ እንደጨረሰች ‹‹..ጀግናዬ የት ነህ?››ስትል ንስሯን ጠራችው.. እየተምዘገዘገ መጣና ከፊት ለፊቷ ካለ የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ አረፈ..
‹‹እሺ ና ተከተለኝ።›› ብላው ወደጥቅጥቁ ጫካ ተራመደች…ወደ ውስጥ ጠልቃ ገባችና የምትፈልገው ቦታ ስትደርስ ከዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ቅጠሎችን እየለመለመች መሬት አነጠፈችና እላዩ ላይ ተደላድላ ተቀመጠች…መጥቶ ከጎኗ ተቀመጠ
‹‹እንድናወራ ነው እዚህ የመጣሁት..››
‹‹እየሰማሀኝ ነው አይደል?›
እየሰማት መሆኑን እንድታውቅ አእምሮን ከፈተላት.
‹‹አዎ እንደዛ ነው…እናቴ እንድትድን አፈልጋለሁ።››
‹‹አይቻልም››የሚል መልስ ሰጣት
‹አይ ይቻላል…አንተ የሆነ ተአምር መስራት አያቅትህም ..ከፈለክ ከአባቴ ጋር ተገናኝና እናቴን ማጣት እንደማልፈልግ ንገረው››
‹‹አይቻልም››ፍርጥም ብሎ መለሰላት፡፡
‹‹ኡፍ..እንግዲያው እሷ ከሞተች እኔም መኖር አልፈልግም…. ይሄንን እወቀው››
‹አንቺ ከሞትሽ እኔም አጠፋለሁ››ብሎ ልክ በሞተችበት ቅፅበት እሱ እንዴት ድርቅርቅ ብሎ እንደሚሞትና ከደቂቃዎች በኃላ መላ አካሉ እንደድቄት ተበታትኖ እንደሚበን አሳያት፡፡ እዝን አላች፡፡
እንዲህ የእሱ ህይወት ከእሷ መኖር ጋር እንደተያያዘና ስትሞት ሟች እንደሆነ ፈፅሞ አታውቅም ነበር..እና እንደዛ በመሆኑ በጣም አዘነች…ቢሆንም ግን ሀሳቧን ለመቀየር ምንም እቅድ የላትም.. መልፈስፈስን አልፈለገችም፡፡
"በጣም እወድሀለሁ.. ታውቃለህ አይደል?.ግን ደግሞ እናቴን ከምንም በላይ ፤ከማንም በላይ ነው ምወዳት እና እንዳልኩህ እናቴ ከሞተች እኛም አብረናት እንሞታለን ማለት ነው።››
የመጨረሻ ውሳኔዋን ከምትናገረው ንግግር ሆነ ከውስጧ ልቧን በማንበብ ከተረዳ በኃላ ከጎኗ ብተት ብሎ ተነሳና ሰማይ ጠቀስ ዛፎችን አልፎ በረረ....ቀጥታ ጭጋጋማውን ደመና አልፎ ተሰወረ.. እዛው በተቀመጠችበት ወደላይ አንጋጣ በአይኖቾ ሸኘችውና ወደትካዜዋ ተመለሰች፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
ይሄ ክስት ከተከሰተ ከ5 ዓመት በኃላ 10ኛ ክፍል ማትሪክ ለመፈተን ዝግጅት ላይ እያለች ድንገት እናትዬው በህይወቷ ለሁለተኛ ጊዜ ክፉኛ ታመመች፡፡ አፋፍሰው ደሎ ሆስፒታል አስገቧት….ወደጎባ ወይም ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ትባላለች ብለው ሲጠብቁ ከሶስት ቀን በኃላ ወደቤት መልሳችሁ ውሰዷት የሚል ትዕዛዝ ተሰጣቸው፡፡
ቀጥታ እየተውረገረገች ዶክተሩ ጋ ገባች፡፡
‹‹አቤት ምን ነበር?›
‹‹ስለእናቴ ጉዳይ ነበር››
‹‹ስለእናትሽ ምን?››
ዝልፍልፍ ብላ ደከማለች እኮ ….በህይወትና በሞት መካከል ሆና እየተመለከታችሁ ወደቤት መልሷት ማለት ምን ማለት ነው...?
ካልቻላቸሁ አልቻልንም ብላችሁ ሪፈር ማለት ነው እንጂ ወደቤት መልሷት ማለት ምን ማለት ነው….?ግልፅ አልሆነልኝም፡፡››
‹እስኪ ተረጋጋግተሸ ተቀመጪና ላስረደዳሽ..እንደው ስታስቢው ይሄንን ቀደም ተከተል ማናውቅ አድርገሽ ነው ምታስቢን ?››
‹‹እኔ እንጃ ግራ አጋባችሁኛ››
‹‹ሁኔታውን እኮ ለአያትሽ አስረድቼቸዋለሁ...እሳቸው ቀስ ብለው ያስረዱሻል፡፡››
‹‹እና እናቴ …የእኔ ውዷ እናት …የሌላ አለም ፈጡርን በፍቅር ጠብ ያደረገችው ተአምረኛዋ እናት እንደቀልድ በአንድ ወር ውስጥ ትሞታለች እያላችሁኝ ነው?››
‹‹አይ እኛ አይደለም እንደዛ ያልነው.. እናትሽ ያለባቸው በሽታ ያለበት ደረጃ እና አሁን ባለው የሳይንስ ግኝት በሽታውን ለማከም ያለንን አቅም ከግምት በማስገባት ነው፡፡››
‹‹እና በቃ ውሳኔያችሁ እንደዛ ነው?››
‹‹አዝናለሁ…ለእሳቸውም የመጨረሻዎቹን ቀናቶች ወዲህ ወዲያ እያሉ ውጤት ለማይኖረው ነገር ከሚንገላቱ በቤተሰባቸው እንክብካቤ ውስጥ ሆነው ቢያሳልፉ ይሻላቸዋል፡፡
‹‹እኔ እናቴን ካዳንኳት…ምን ትላለህ?››
‹‹ስለአንቺ የሰማሁትን ለማመን እገደዳለሁ››
‹‹ስለእኔ ምን ሰማህ?››በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹የመላዕክት ዝርያ እንዳለብሽ››
‹‹አይ ያሉህ እንኳን እንደዛ አይደለም…የደቢሎስ ዝርያ አለባት ነው ሊሉህ የሚችሉት፡፡››
‹‹ያው ነው…ዳቢሎስም ሌላ ምንም ሳይሆን መላዐክ ነው…ለዛውም ከዋናዎቹ አንድና ዋነኛው የነበረ.በተወሰነ ያለመግባባት ከእግዚያብር የመኖሪያ ግዛት የተሰደደ…››
‹‹የተናገርከው ከልብህ ስለሆነ አስደስተሀኛል…ለማንኛውም ስለጮህኩብህ ይቅርታ.. እናቴን ወደቤት ወስዳታለሁ...እናም አድናታለሁ።››
‹‹እንግዲህ እንዳልኩሽ ነው….ለማንኛውም እቤት ብቅ እያልኩ አያቸዋለሁ..ድንገተኛ ነገር ተፈጥሮ ከፈለግሺኝም ደውይልኝ› ብሎ ቁጥሩን ሰጣት ተቀበለችውና አመስግናለሁ ብላ ወጣች፡፡
ወዲያው ነበር እናቷን ይዛ ወደቤት የገባችው፡፡ግርግሩ ጋብ ሲል ወደ እናቷ መኝታ ቀረበችና…በቀናቶቸ በሽታ የሰለሉና የደከሙ እጆቾን በእጆቾ ውስጥ አስገብታ እየዳበሰች፡፡
‹‹ሀርሜ አይዞሽ እኔ ምንም እንድትሆኚ አልፈቅድም››
‹‹ልጄ በዚህ ጉዳይ እንድትጨነቂ አልፈልግም…እንደውም መሄድ እፈልጋለሁ።››ስትል መለሰችላት፡፡
እማ ምን ማለት ነው …እኔን ጥለሽ ወደየት ነው የምትሄጂው…አንቺ ከሌለሽ እኮ እኔም መኖር በጣም ነው የሚከብደኝ …ማን ነው የሚረዳኝ?›
‹‹ልጄ አንቺ የአባትሽ ልጅ ነሽ. .በጣም ጠንካራና የማትሰበሪ ነሽ…እኔ ብሄድ ምን አልባት አባትሽን አገኘው ይሆናል፡፡ምን አልባት መልሰን አንድ ላይ የመሆን እድል እናገኝ ይሆናል፡፡
‹አይ እንደዛ አይሆንም…የእሱ አለምና አንቺ ስትሞቺ የምትሄጂበት ቦታ አንድ መሆኑን በምን እርግጠኛ ሆንሽ? እንዲህ አይነት ቁማርማ እንድትጫወቺ አልፈቅድም..በይ አሁን ደክሞሻል.. እረፊ .የሆነ ቦታ ደርሼ መጣሁ…››
‹‹ደግሞ ወዴት ልትሄጂ ነው?››
‹‹እማ ደግሞ የሆነ ቦታ አልኩሽ እኮ›ብላ ግንባሯን በመሳም ወጥታ ሄደች.. ግቢውን እንደለቀቀች ከጀርባዋ ንሰሯ እየተምዘገዘገ መጥቶ ተከሻዋ ላይ አረፈ.እርምጃዋን እልገታችም….በሀሳብ እየተብሰለሰለች ቀጥታ ከተማውን ለቃ ወደ ያዶት ወንዝ ነው የሄደችው…እናትና አባቷ ተገናኝተውበት ወደነበረ ልክ እንደቤተመቅደስ እያየች ወደ አደገችበት ቦታ ነው የሄደችው፡፡እንደደረሰች ንስሯ ከትከሻዋ ለቆ ተነሳና በአካበባቢው ካሉት ብዛት ያላቸው ግዙፉ ዛፎች መካከል አንዱ ላይ አረፈ.እሷም ልብሷን አወላልቃ ዛፉ ላይ እስከግማሽ እየተንጠላጠለችና እየተሳበች ወጣችና አስር ሜትር ከፍታ ላይ ከደረሰች በኃላ ዘላ እየተምዘገዘገች ወንዙ ውስጥ ቦጭረቅ ብላ ገባች…ከዛ ወደውስጥ ሰመጠችና የሆነ ሚስጥራዊ ምርምር እንደሚያካሂድ የባህር ውስጥ አሳሽ ውስጥ ለውስጥ ትንፋሿን ተቆጣጥራ ከወዲህ ወዲያ እየተመላለሰች.፡፡
ግማሽ ለሚሆን ሰዓት ከዋኘች በኃላ የድካም ስሜት ሲሰማት ወጥታ ልብሷን ለበሰች፡፡የመጨናነቅ ስሜቷ አሁን ቀለል ብሏታል…ወደዚህ ቦታ የምትመጠጣው ለመታደስ ነው.ከአባቷ መንፈስ ጋር ለመገናኘት..እሱ የረገጣቸውን የወንዙን ወለል ለመርገጥ ፤እሱ የተነፈሰባቸውን ቦታዎች እሷም ልትተነፍስባቸውና ከእሱ ጋር ያላትን የመንፈስ መስተጋብር ለማጎልበት ነው....እናም ደግሞ ምን አልባት አንድ ቀን ቡልቅ ብሎ ከዚህ ከውሀው መሀል በመውጣት ተጠምጥሞ ይስመኛል…በሚል ድብቅ ምኞትም በመጓጓት ነው እንደዛ የምታደረግው;፡
ለባብሳ እንደጨረሰች ‹‹..ጀግናዬ የት ነህ?››ስትል ንስሯን ጠራችው.. እየተምዘገዘገ መጣና ከፊት ለፊቷ ካለ የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ አረፈ..
‹‹እሺ ና ተከተለኝ።›› ብላው ወደጥቅጥቁ ጫካ ተራመደች…ወደ ውስጥ ጠልቃ ገባችና የምትፈልገው ቦታ ስትደርስ ከዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ቅጠሎችን እየለመለመች መሬት አነጠፈችና እላዩ ላይ ተደላድላ ተቀመጠች…መጥቶ ከጎኗ ተቀመጠ
‹‹እንድናወራ ነው እዚህ የመጣሁት..››
‹‹እየሰማሀኝ ነው አይደል?›
እየሰማት መሆኑን እንድታውቅ አእምሮን ከፈተላት.
‹‹አዎ እንደዛ ነው…እናቴ እንድትድን አፈልጋለሁ።››
‹‹አይቻልም››የሚል መልስ ሰጣት
‹አይ ይቻላል…አንተ የሆነ ተአምር መስራት አያቅትህም ..ከፈለክ ከአባቴ ጋር ተገናኝና እናቴን ማጣት እንደማልፈልግ ንገረው››
‹‹አይቻልም››ፍርጥም ብሎ መለሰላት፡፡
‹‹ኡፍ..እንግዲያው እሷ ከሞተች እኔም መኖር አልፈልግም…. ይሄንን እወቀው››
‹አንቺ ከሞትሽ እኔም አጠፋለሁ››ብሎ ልክ በሞተችበት ቅፅበት እሱ እንዴት ድርቅርቅ ብሎ እንደሚሞትና ከደቂቃዎች በኃላ መላ አካሉ እንደድቄት ተበታትኖ እንደሚበን አሳያት፡፡ እዝን አላች፡፡
እንዲህ የእሱ ህይወት ከእሷ መኖር ጋር እንደተያያዘና ስትሞት ሟች እንደሆነ ፈፅሞ አታውቅም ነበር..እና እንደዛ በመሆኑ በጣም አዘነች…ቢሆንም ግን ሀሳቧን ለመቀየር ምንም እቅድ የላትም.. መልፈስፈስን አልፈለገችም፡፡
"በጣም እወድሀለሁ.. ታውቃለህ አይደል?.ግን ደግሞ እናቴን ከምንም በላይ ፤ከማንም በላይ ነው ምወዳት እና እንዳልኩህ እናቴ ከሞተች እኛም አብረናት እንሞታለን ማለት ነው።››
የመጨረሻ ውሳኔዋን ከምትናገረው ንግግር ሆነ ከውስጧ ልቧን በማንበብ ከተረዳ በኃላ ከጎኗ ብተት ብሎ ተነሳና ሰማይ ጠቀስ ዛፎችን አልፎ በረረ....ቀጥታ ጭጋጋማውን ደመና አልፎ ተሰወረ.. እዛው በተቀመጠችበት ወደላይ አንጋጣ በአይኖቾ ሸኘችውና ወደትካዜዋ ተመለሰች፡፡
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
አስር ሠዓት ከሃያ ሲሆን ሻንጣቸውን ጭነው ሆቴሉን ተሠናብተው ወጡ፡፡ ቁልቁለታማውን ኮረኮንች መንገድ ጨርሰው ዋናው አስፓልት መንገድ ሊገቡ ሃምሳ ሜትር ገደማ ሲቀራቸው ወደ ገበሬዎች ሆቴል አጥር መኪናውን ጥግ አሲይዞ አቆመና ተንቀሳቃሽ ስልኩን ከኪሱ አውጥቶ መደወል ጀመረ፡፡
‹‹ሄሎ ፎዚ››
‹‹ደህና ነኝ››
<<እ .. ምን አልሺኝ?››
‹‹አግኝቻታለሁ...ዝርዝር ሁኔታውን ማታ ስመጣ አወራሻለሁ፡፡ አሁን የደወልኩት እንደምንም ብለሽ ለአስር ሠው የሚበቃ እራት ማዘጋጀት ትቺይ እንደሆነ ልጠይቅሽ ነው?››
‹‹ጎሽ... ብር የሚያንስሽ ከሆነ ከሰሎሞን ውሰጂ ፤ደውዬ እነግረዋለሁ››
‹‹ቻው... ሁለት ሠዓት አካባቢ እንደርሳለን፡፡››
በተቀመጠችበት ደንዝዛ በፍራቻና በሀዘኔታ የሚሠራውን ታስተውላለች፡፡ አዝማሚያው አላማራትም፡፡ እንዲህ የጓጓለትን ነገር ሲያጣ ተስፋ በመቁረጥ አንድ ነገር እንዳይሆን ፈራች፡፡ እሱ አንድ ነገር ከሆነ ደግሞ እሷ እራሷን ይቅር ማለት እንደማትችልና የከፋ ውሳኔ ላይ እንደምትደርስ ሲታሠባት ሠውነቷ ተንቀጠቀጠ፡፡ ሁሴን ሁለተኛ ስልኩን እያናገረ ነው …፡፡
‹‹አንተ ቦርጫም አመንክም አላመንክም ሁለት ሠዓት ላይ እቤቴ ይዣት ከች ነው፡፡››
‹‹ግዴለህም በእርግጠኝነት ማንነቷን ለይቼዋለሁ፤ ከአስር ደቂቃ በኋላ በእጄ ነች፡፡››
‹‹ኡፍ ... አሁን ክርክሩን ተውና ቤት ሄደህ ፎዚያን አግዛት፤ ባዶ ቤት ይዣት መምጣት አልፈልግም፤ እሺ ካለች ለኤደንም ንገራት ፤ሁለት ሠዓት ቤት እንድትገኝ፤ ቅር ካላለህ የውብዳርንም ደውዬ ብጠራት፡፡››
<< ... በቃ በቃ ትቼዋለሁ ..ቻው በቃ በሠዓቱ እንገናኝ፡፡››
ስልኩን አናግሮ ሲጨርስ መልሶ ኪሱ ከተተና መኪናውን አስነስቶ ወደ አስፓልቱ ገባና ወደ ግራ ታጥፎ አዲስ አበባ መውጫ ላይ ወደሚገኘው ፒራሚድ ሆቴል አመራ፡፡ምንም ሳይነጋገሩ ነበር ሆቴሉ ደርሠው ከመኪና በመውረድ የግቢውን ውስጥ ጠቅላላ ማየት የሚቻልበት ቦታ መርጠው የተቀመጡት፡፡ ትንግርት ደመነፍሷ ነው እየተንቀሳቀሰ ያለው፤ አዕምሮዋ ራሱ ማሠብ ያቆመ መስሎ ተሰማት፡፡
ሁሴን‹‹አየሻት አይደል?›› አላት በፈገግታ እንደተሞላ ፡፡
‹‹ማን..ን?›› አለችው ከደነዘዘችበት ባና፡፡
‹‹ማንን ነው ለማየት የመጣነው? ሚሥጥርን ነዋ፡፡ ከፊት ለፊትሽ አትታይሽም?››
በመከራ አንገቷን ካቀረቀረችበት አቅንታ አይኖቿን ወደ ጠቆማት አቅጣጫ ወረወረች፡፡ እውነትም ጠይሟ ወጣት በተመሳሳይ ሁኔታ ወይኗን እየተጎነጨች መጽሀፏን ታነባለች፡፡ ትንግርት እሷን በምታይበት ሠዓት እሷም አማትራ እነሱን ተመለከተችና እጇ ላይ ያሠረችውን ሠዓት በማየት ወደ ንባቧ ተመለሠች፡፡
‹‹ሠዓቷን እያየች ነው፤በማርፈድህ ቅር ሳይላት አይቀርም፡፡››
‹‹ዋናው አለመቅረቴ ነው ...>> አስተናጋጁ አቋረጣቸው... ሁለቱም ጭማቂ አዘዙና መጣላቸው፡፡
‹‹አበባውን ይዘሻል አይደል?››በዝምታ ቦርሳዋን ከፈተችና የመጨረሻው ዕድል መግለጫ የሆነችውን አበባ ሠጠችው፡፡ ‹‹ከበስተጀርባህ አሮጊቷ እንዳለች እንዳትዘነጋ፡፡›› አለችው፡፡
ቀስ ብሎ ወደ ጀርባው ሲገላመጥ እውነትም
ዛሬም ያን ቦርጯን ወደ ፊት አንገፍጥጣ አይኗን ጀርባው ላይ ተክላለች፡፡ሁሴን ፈጎ የዋለ ፊቱን በመጠኑ ቋጠረው ‹‹ይህቺ ክምርማ
እኔን አታጭበረብረኝም፡፡››
‹‹አጭበርባሪዋ የትኛዋ እንደሆነች በምን አወክ? ምን አልባት ይህቺ ጠይሞም ሚሥጥር ላትሆን ትችላለች፡፡ ምን አልባት ሁለቱም አጭበርባሪ ይሆናሉ፡፡››
‹‹እንግዲያው ሁለቱም አጭበርባሪዎች ከሆኑ ትክክለኛዋ ሚሥጥር አንቺ ነሽ ማለት ነው?››
ልትጠጣ ያለችው የጁስ ብርጭቆ ከእጇ ተንሸራቶ አመለጣት… እሱ በፍጥነት ባይቀልበው ኖሮ መሬት ወድቆ ተከስክሶ ነበር
‹‹ምን ነካሽ እያንቀላፋሽ ነው እንዴ? አየሽ ዛሬ ማዳመጥ የምፈልገው ስሜቴን ነው፤ስሜቴ ደግሞ ይህቺ ጠይም ወጣት ትክክለኛዋ የእኔዋ ሚሥጥር መሆኗን ነግሮኛል፡፡››
‹‹ታዲያ እርግጠኛ ከሆንክ ምን ትጠብቃለህ ተነስና አበባውን ስጣት፤ ሀብሉን አንገትህ ላይ ታጥልቅልህ፤ አንተም ቀለበቱን በጣቷ ላይ ሠካላት… እንደውም ጣቶቿ በጣም ያምራሉ››
‹‹ምን አስቸኮለሽ፤ ገና አንድ ሠዓት አለኝ፡፡ ልክ አስር ደቂቃ ሲቀረው ነው አበባውን የምሠጣት እስከዛ እኔ በጉጉት እንዳተሠቃየሁ እሷም ትንሽ ትሠቃይ፡፡››
‹‹እስከዛ ደንዝዘን ቁጭ እንበል?›› አለችው ትንግርት ተስፋው በተሟጠጠ ድምፅ፡፡
‹‹እኔ ለሠላሳ ደቂቃ ያህል የነገሮችን አጀማመርና አሁን ያሉበትን ሁኔታ ወደ ኃላ ተመልሼ ማሠብ እፈልጋለሁ፡፡ አስር ደቂቃ ሲቀረው አስታውሺኝ›› በማለት አይኖቹን ሠማይ ላይ ተክሎ እግሮቹን አንፈራጦ ሀሳብ ውስጥ ገባ፤ ከሚሥጥር እንዴት ፍቅር እንደያዘው፤ ከእሷ ጋር የተለዋወጣቸው የስልክ ምልልሶች፤ እሷን ለማግኘት
የተጋፈጣቸው ውጣ ውረዶች፤አንድ በአንድ
በቅደም ተከተል ማሠላሠል ጀመረ፡፡
በመሀከል ዓይኖቹን ወደ ጠይሟ አንባቢ ወጣት ይወረውራቸዋል መልሶ ወደ ሀሳብ ይገባል፡፡ሙሉ በሙሉ ከሀሳብ ተጎትቶ የወጣው ትንግርት ትከሻውን ስትነቀንቀው ነበር፡፡ ‹‹ሠዓቱ ደርሷል›› አለችው
በሚርገበገብ ድምፅ፡፡ሠዓቱን ተመለከተ፡፡
በእጁ የያዘውን ቀይ የፈነዳ አበባም አስተዋለ፤
እላዩ ላይ የተለጠፈውን እንቆቅልሽ የሚል ፅሁፍም ለመቶኛ ጊዜ ደግሞ ተመለከተ …፡፡
‹‹አጨበጨበና አስተናጋጁን ጠራ.... ያቺ የምታነበው ልጅ ትታይሀለች የእሷን እና ከጀርባዋ የተቀመጠችውን ወፍራም ሴትዬ ሂሳብ ስንት ነው፡፡ የእኛንም ጨምረህ ቢል አሠራ፡፡›› አስተናጋጁ ወደ ዋናው ሆቴል
እየተጣዳፈ ሄዶ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ቢል ይዞለት መጣ፡፡
መቶ ሠማንያ ስምንት ብር ከሃማሳ ሳንቲም ....ሁለት መቶ ብር አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ ወረወረና ወደ ትንግርት ዞሮ‹‹ቦርሳሽን ያዥና ተነሽ›› አላት፡፡
በድንጋጤ አንጋጣ አየችው፡፡
‹‹ተነሽ እኮ ነው የምልሽ፡፡›› ግራ እጇን ይዞ እየተጣደፈ ግቢው ውስጥ ወደ ቆመችው መኪናው ይዟት ገባ፡፡ መኪናውን ከግቢው አውጥቶ ፊቷን ወደ አዲስ አበባ በማዞር ወደ ዋናው አስፓልት ገብቶ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ በኋላ ማሳያ ስፖኪዬው ሲመለከት ጠይሟ ወጣት እና አሮጊቷ ጎን ለጎን ቆመው አይናቸውን እሱ መኪና ላይ ተክለው በመገረም ሲመለከቱት አያቸው፡፡
ትንግርትም በድንጋጤና በሠመመን ውስጥ ሆና ያለ ምንም እንቅስቃሴና ንግግር
ደንዝዛለች፡፡ ዓኖቿ ፊት ለፊት ያለው አስፓልት ላይ ተተክለዋል፡፡ ጥያቄም ሆነ አስተያየት መሠንዘር አልቻለችም፡፡ መኪናዋን
በመጨረሻው ፍጥነት እያስፈተለከ ነው፡፡
ያበደም መሰላት፤ ‹‹ሁለታችንንም ወደ ግብዓተ መሬታችን ይዞን እየተጓዘ ነው እንዴ?››ስትል አሰበች…በጣም ፈራች፡፡...
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
አስር ሠዓት ከሃያ ሲሆን ሻንጣቸውን ጭነው ሆቴሉን ተሠናብተው ወጡ፡፡ ቁልቁለታማውን ኮረኮንች መንገድ ጨርሰው ዋናው አስፓልት መንገድ ሊገቡ ሃምሳ ሜትር ገደማ ሲቀራቸው ወደ ገበሬዎች ሆቴል አጥር መኪናውን ጥግ አሲይዞ አቆመና ተንቀሳቃሽ ስልኩን ከኪሱ አውጥቶ መደወል ጀመረ፡፡
‹‹ሄሎ ፎዚ››
‹‹ደህና ነኝ››
<<እ .. ምን አልሺኝ?››
‹‹አግኝቻታለሁ...ዝርዝር ሁኔታውን ማታ ስመጣ አወራሻለሁ፡፡ አሁን የደወልኩት እንደምንም ብለሽ ለአስር ሠው የሚበቃ እራት ማዘጋጀት ትቺይ እንደሆነ ልጠይቅሽ ነው?››
‹‹ጎሽ... ብር የሚያንስሽ ከሆነ ከሰሎሞን ውሰጂ ፤ደውዬ እነግረዋለሁ››
‹‹ቻው... ሁለት ሠዓት አካባቢ እንደርሳለን፡፡››
በተቀመጠችበት ደንዝዛ በፍራቻና በሀዘኔታ የሚሠራውን ታስተውላለች፡፡ አዝማሚያው አላማራትም፡፡ እንዲህ የጓጓለትን ነገር ሲያጣ ተስፋ በመቁረጥ አንድ ነገር እንዳይሆን ፈራች፡፡ እሱ አንድ ነገር ከሆነ ደግሞ እሷ እራሷን ይቅር ማለት እንደማትችልና የከፋ ውሳኔ ላይ እንደምትደርስ ሲታሠባት ሠውነቷ ተንቀጠቀጠ፡፡ ሁሴን ሁለተኛ ስልኩን እያናገረ ነው …፡፡
‹‹አንተ ቦርጫም አመንክም አላመንክም ሁለት ሠዓት ላይ እቤቴ ይዣት ከች ነው፡፡››
‹‹ግዴለህም በእርግጠኝነት ማንነቷን ለይቼዋለሁ፤ ከአስር ደቂቃ በኋላ በእጄ ነች፡፡››
‹‹ኡፍ ... አሁን ክርክሩን ተውና ቤት ሄደህ ፎዚያን አግዛት፤ ባዶ ቤት ይዣት መምጣት አልፈልግም፤ እሺ ካለች ለኤደንም ንገራት ፤ሁለት ሠዓት ቤት እንድትገኝ፤ ቅር ካላለህ የውብዳርንም ደውዬ ብጠራት፡፡››
<< ... በቃ በቃ ትቼዋለሁ ..ቻው በቃ በሠዓቱ እንገናኝ፡፡››
ስልኩን አናግሮ ሲጨርስ መልሶ ኪሱ ከተተና መኪናውን አስነስቶ ወደ አስፓልቱ ገባና ወደ ግራ ታጥፎ አዲስ አበባ መውጫ ላይ ወደሚገኘው ፒራሚድ ሆቴል አመራ፡፡ምንም ሳይነጋገሩ ነበር ሆቴሉ ደርሠው ከመኪና በመውረድ የግቢውን ውስጥ ጠቅላላ ማየት የሚቻልበት ቦታ መርጠው የተቀመጡት፡፡ ትንግርት ደመነፍሷ ነው እየተንቀሳቀሰ ያለው፤ አዕምሮዋ ራሱ ማሠብ ያቆመ መስሎ ተሰማት፡፡
ሁሴን‹‹አየሻት አይደል?›› አላት በፈገግታ እንደተሞላ ፡፡
‹‹ማን..ን?›› አለችው ከደነዘዘችበት ባና፡፡
‹‹ማንን ነው ለማየት የመጣነው? ሚሥጥርን ነዋ፡፡ ከፊት ለፊትሽ አትታይሽም?››
በመከራ አንገቷን ካቀረቀረችበት አቅንታ አይኖቿን ወደ ጠቆማት አቅጣጫ ወረወረች፡፡ እውነትም ጠይሟ ወጣት በተመሳሳይ ሁኔታ ወይኗን እየተጎነጨች መጽሀፏን ታነባለች፡፡ ትንግርት እሷን በምታይበት ሠዓት እሷም አማትራ እነሱን ተመለከተችና እጇ ላይ ያሠረችውን ሠዓት በማየት ወደ ንባቧ ተመለሠች፡፡
‹‹ሠዓቷን እያየች ነው፤በማርፈድህ ቅር ሳይላት አይቀርም፡፡››
‹‹ዋናው አለመቅረቴ ነው ...>> አስተናጋጁ አቋረጣቸው... ሁለቱም ጭማቂ አዘዙና መጣላቸው፡፡
‹‹አበባውን ይዘሻል አይደል?››በዝምታ ቦርሳዋን ከፈተችና የመጨረሻው ዕድል መግለጫ የሆነችውን አበባ ሠጠችው፡፡ ‹‹ከበስተጀርባህ አሮጊቷ እንዳለች እንዳትዘነጋ፡፡›› አለችው፡፡
ቀስ ብሎ ወደ ጀርባው ሲገላመጥ እውነትም
ዛሬም ያን ቦርጯን ወደ ፊት አንገፍጥጣ አይኗን ጀርባው ላይ ተክላለች፡፡ሁሴን ፈጎ የዋለ ፊቱን በመጠኑ ቋጠረው ‹‹ይህቺ ክምርማ
እኔን አታጭበረብረኝም፡፡››
‹‹አጭበርባሪዋ የትኛዋ እንደሆነች በምን አወክ? ምን አልባት ይህቺ ጠይሞም ሚሥጥር ላትሆን ትችላለች፡፡ ምን አልባት ሁለቱም አጭበርባሪ ይሆናሉ፡፡››
‹‹እንግዲያው ሁለቱም አጭበርባሪዎች ከሆኑ ትክክለኛዋ ሚሥጥር አንቺ ነሽ ማለት ነው?››
ልትጠጣ ያለችው የጁስ ብርጭቆ ከእጇ ተንሸራቶ አመለጣት… እሱ በፍጥነት ባይቀልበው ኖሮ መሬት ወድቆ ተከስክሶ ነበር
‹‹ምን ነካሽ እያንቀላፋሽ ነው እንዴ? አየሽ ዛሬ ማዳመጥ የምፈልገው ስሜቴን ነው፤ስሜቴ ደግሞ ይህቺ ጠይም ወጣት ትክክለኛዋ የእኔዋ ሚሥጥር መሆኗን ነግሮኛል፡፡››
‹‹ታዲያ እርግጠኛ ከሆንክ ምን ትጠብቃለህ ተነስና አበባውን ስጣት፤ ሀብሉን አንገትህ ላይ ታጥልቅልህ፤ አንተም ቀለበቱን በጣቷ ላይ ሠካላት… እንደውም ጣቶቿ በጣም ያምራሉ››
‹‹ምን አስቸኮለሽ፤ ገና አንድ ሠዓት አለኝ፡፡ ልክ አስር ደቂቃ ሲቀረው ነው አበባውን የምሠጣት እስከዛ እኔ በጉጉት እንዳተሠቃየሁ እሷም ትንሽ ትሠቃይ፡፡››
‹‹እስከዛ ደንዝዘን ቁጭ እንበል?›› አለችው ትንግርት ተስፋው በተሟጠጠ ድምፅ፡፡
‹‹እኔ ለሠላሳ ደቂቃ ያህል የነገሮችን አጀማመርና አሁን ያሉበትን ሁኔታ ወደ ኃላ ተመልሼ ማሠብ እፈልጋለሁ፡፡ አስር ደቂቃ ሲቀረው አስታውሺኝ›› በማለት አይኖቹን ሠማይ ላይ ተክሎ እግሮቹን አንፈራጦ ሀሳብ ውስጥ ገባ፤ ከሚሥጥር እንዴት ፍቅር እንደያዘው፤ ከእሷ ጋር የተለዋወጣቸው የስልክ ምልልሶች፤ እሷን ለማግኘት
የተጋፈጣቸው ውጣ ውረዶች፤አንድ በአንድ
በቅደም ተከተል ማሠላሠል ጀመረ፡፡
በመሀከል ዓይኖቹን ወደ ጠይሟ አንባቢ ወጣት ይወረውራቸዋል መልሶ ወደ ሀሳብ ይገባል፡፡ሙሉ በሙሉ ከሀሳብ ተጎትቶ የወጣው ትንግርት ትከሻውን ስትነቀንቀው ነበር፡፡ ‹‹ሠዓቱ ደርሷል›› አለችው
በሚርገበገብ ድምፅ፡፡ሠዓቱን ተመለከተ፡፡
በእጁ የያዘውን ቀይ የፈነዳ አበባም አስተዋለ፤
እላዩ ላይ የተለጠፈውን እንቆቅልሽ የሚል ፅሁፍም ለመቶኛ ጊዜ ደግሞ ተመለከተ …፡፡
‹‹አጨበጨበና አስተናጋጁን ጠራ.... ያቺ የምታነበው ልጅ ትታይሀለች የእሷን እና ከጀርባዋ የተቀመጠችውን ወፍራም ሴትዬ ሂሳብ ስንት ነው፡፡ የእኛንም ጨምረህ ቢል አሠራ፡፡›› አስተናጋጁ ወደ ዋናው ሆቴል
እየተጣዳፈ ሄዶ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ቢል ይዞለት መጣ፡፡
መቶ ሠማንያ ስምንት ብር ከሃማሳ ሳንቲም ....ሁለት መቶ ብር አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ ወረወረና ወደ ትንግርት ዞሮ‹‹ቦርሳሽን ያዥና ተነሽ›› አላት፡፡
በድንጋጤ አንጋጣ አየችው፡፡
‹‹ተነሽ እኮ ነው የምልሽ፡፡›› ግራ እጇን ይዞ እየተጣደፈ ግቢው ውስጥ ወደ ቆመችው መኪናው ይዟት ገባ፡፡ መኪናውን ከግቢው አውጥቶ ፊቷን ወደ አዲስ አበባ በማዞር ወደ ዋናው አስፓልት ገብቶ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ በኋላ ማሳያ ስፖኪዬው ሲመለከት ጠይሟ ወጣት እና አሮጊቷ ጎን ለጎን ቆመው አይናቸውን እሱ መኪና ላይ ተክለው በመገረም ሲመለከቱት አያቸው፡፡
ትንግርትም በድንጋጤና በሠመመን ውስጥ ሆና ያለ ምንም እንቅስቃሴና ንግግር
ደንዝዛለች፡፡ ዓኖቿ ፊት ለፊት ያለው አስፓልት ላይ ተተክለዋል፡፡ ጥያቄም ሆነ አስተያየት መሠንዘር አልቻለችም፡፡ መኪናዋን
በመጨረሻው ፍጥነት እያስፈተለከ ነው፡፡
ያበደም መሰላት፤ ‹‹ሁለታችንንም ወደ ግብዓተ መሬታችን ይዞን እየተጓዘ ነው እንዴ?››ስትል አሰበች…በጣም ፈራች፡፡...
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሳምንት ሙሉ ታገስኩ….ላብድ ደረስኩ…ስራ ሁሉ መስራት አቃተኝ….ከ15ቀን በኋላ ሰውዬውን የሆነ ስብሰባ ሲመራ በቲቪ አየሁት….ደስ አለኝ፡፡ልክ እሷን ያገኘሁ ነው የመሰለኝ…..በቃ እሷም መጥታለች ማለት ነው ስል አሰብኩ….ማንንም እንዳታገኝ ቤት ውስጥ ቆልፎባታል ስል በማሰብ እርግጠኛ ወደመሆን ተሸጋገርኩ እሷን ነፃ ለማውጣት ወሰንኩ፡፡ ጓደኞቼን እንዲረዱኝ ጠየቅኩ፡፡ የሰውየውን ቤት ቀንና ሌሊት ማጥናትና መሰለል ጀመርን፤የሚገባውንና የሚወጣውን ሁሉ መከታተል ቀጠልን…በአራተኛው ቀን ቤቱ ያሉት አንድ የቤት ሰራተኛ አንድ ነርስ እና አንድ ህፃን ልጅ ብቻ እንደሆኑ አረጋገጥን›› የምሆነውም የማደርገውም ነገር ግራ ገባኝ…ሰራተኛዋ እቃ ለመግዛት ከቤት ስትወጣ ጠብቀን አገትናትና አስፈራርተን መረጃ ጠየቅናት..ሴትዬዋም ፈርታ ስለነበረ የምታውቀውን ሁሉ ምንም ሳታስቀር ዘረዘረችልን፡፡
‹‹ምን አለቻችሁ ?ምን ሆና ነው?››ሳባ የተፈጠረውን ለማወቅ በጉጉት ጠየቀች፡፡
‹‹ሚስቱ ከአሜሪካ ወደሀገሬ አልመለስም ብላ አንደኛውን ልጅ ይዛበት እንደተሰወረች..ለ15 ቀን ከዛሬ ነገ ተመልሳ ትመጣለች ብሎ ሲጠብቃትና ሲያስፈልጋትም ከቆየ በኋላ ተስፋ ቆርጦ የተወችለትን አንደኛውን ልጁን ይዞ ወደ ሀገር እንደተመለሰ እንደነገራቸው፣…እና ሁልጊዜ ወደቤት ሲገባ እሱን እያሰበ እንደሚያዝንና እንደሚተክዝ ነገረችን….ላምን አልቻልኩም፡፡
በሰማሁት ዜና በጣም ተረበሽኩ..ላብድ ደረስኩ‹‹እሷ በፍፁም እንደዛ አታደርግም..አንደዛ ብታደርግ ኖሮ ቢያንስ ካለችበት ቦታ ለእኔ የሆነ መልዕክት ትልክልኝ ነበር…ኢሜሌንም ሁለቱንም ስልክ ቁጥሬን በቃሏ ልክ እንደገዛ ስሟ ነው የምታውቀው….እና የሆነ ነገር እንደሆነች ገባኝ፡፡ በህይወቴ ወሰንኩና እሷ ምን እንደሆነች ለመረዳት አንድ አደገኛ ነገር ለማድረግ ወሰንኩ በሁለት ቦዲጋርድ እየታጀበ ወደቤቱ የሚመጣውንና የሚሄደውን ሚኒስቴር ዲኤታ በጓደኞቼ እገዛ ቤት ውስጥ ገብቼ በገዛ መኝታ ቤቱ ለመተኛት ሲገባ ጠበቅኩና ሽጉጥ ግንባሩ ላይ ደቅኜ እጆቹንና እግሮቹን ጠፍሬ ከወንበር ጋር አሰርኩትና እውነቱን እንዲነግረኝ ጠየቅኩት››
‹አንተ ነህ ማለት ነው ውሽማዋ?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
‹‹ሚስትህን እንደዛ አይነት ስህተት ውስጥ እንድትገባ የገፋፋሀት አንተው ነህ
…ምንም አይነት ለአሷ የሚሆን ጊዜ አልነበረህም….››አልኩት፡፡
‹‹እና በእኔ ላይ መሸርሞጧ ትክክል ነው ትላለህ?››
‹‹አንተም እኮ ስፍር ቁጥር ከሌላቸው ሴቶች ጋር በየሆቴሉና ሎጁ ስትቀብጥና ስትሸረሙጥ መኖርህን አውቃለሁ…ከፈለክ መረጃው አለኝ….አልኩና ሞባይሌ ላይ ከነበሩት አንድ ሶስት መረጃዎች ውስጥ ከፈትኩና አሳየሁት›
‹‹እና እኔ ስላደረኩት እሷ ማድረግ አለባት እያልክ ነው…?ደግሞ ቢያንስ እኔ እኮ ልጅ ወልጄ አላመጣሁባትም››
‹‹አይ አንተም ንፁህ አይደለህም ስለዚህ ይቅርታ ይገባታል እያልኩህ ነው…አሁን የት ነው የቆለፍክባት?››
‹‹የምን መቆለፍ…ጉዷ ተፍረጥርጦ ሲወጣ እዛው አሜሪካ ነው አንደኛውን ልጇን ይዛ የተሰወረችው›› ብሎ ሊያታልለኝ ሞከረ….ብዙ ሞከርኩ ሲያስቸግረኝ አፉን አፈንኩትና ገልብጬ እግሩ እስኪተለተል ወፌ ላላ ስገርፈው…በመጨረሻ አመነልኝ፡፡ ሲጨቃጨቅ ድንገት እንደመታትና እንደሞተችበት…ከዛ ለአሜሪካ ጋንግስተሮቸ ብዙ ብር ከፍሎ እሬሳዋ እንዲወገድ እንዳደረገ እና የእሱ ያልሆነውን ልጁም ነጥሎ ለማደጎ ድርጅቶች እንደሰጠ አፉን ሞልቶ ነገረኝ….ልጁን የሰጠበትን የማደጎ ድርጅት አድራሻ ተቀበልኩትና ልገድለው ፈለኩ፤ከራሴ ጋር ለበርካታ ደቂቃዎች ተሟገትኩ ግን የልጄ ወንድም አባት ነው…እንዴት ምንም ያማያውቀውን ህፃን ያለእናት መቅረቱ ሳያንስ ያለአባት አስቀረዋለሁ? ብዬ አሰብኩ….፡፡
ከዛ ስለእኔ ለሌላ ሰው ቢያወራ ሊበቀለኝ ሙከራ ቢያደርግ እሱንም አሳልፌ እንደምሰጠው ስልጣኑንም ክብሩንም አጥተን እስር ቤት እንዲበሰብስ እንደማደርገው ነግሬ በገባሁበት ቦታ ጋርዶቹ ሳያዩኝ ጥዬው ወጣሁ፡፡
‹‹እና አላሳሰርከውም?››
‹‹ባሳስረው ምን ይጠቅመኛል…?አራስ ልጅ እኮ አለው...ልጁ ደግሞ ምንም ቢሆን የእሷ ነው››
‹‹ከዛ በኋላ ሊያጠቃህ አልሞከረም?››
‹‹በፍፁም ስሬ ድርሽ አላለም፡፡››
‹‹እና ልጅህን የምታስመልስበት ምንም መንገድ አላገኘህም?.››
አሜሪካ በሚገኙ ወዳጆቼ አማካይነት ለረጅም ጊዜ ካፈላለኩ በኃላ የዛሬ ወር አካባቢ ትክክለኛ አድርሻውን አገኘሁ፡፡››
‹‹በእውነት ደስ ሲል..››
‹አዎ ደስ ይላል.. እሱ ለማደጎ ድርጅት ቢያስረክበውም .ማደጎ ድርጅቱ ደግሞ አሳዳጊ አግኝቶ ለአንድ አሜሪካዊ ጥንዶች አስተላልፈው ስለሰጡት አሁን በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ማወቅ ችያለሁ…..እግዜር ካለ በቅርብ ሄጄ እንደማየውና ከተቻለ ይዤው እንደምመጣ ከልሆነ እንኳን ከወላጆቹ ጋር ተዋውቄ ልጄንም አይቼ መምጣት ፈልጋለሁ..፡፡
‹‹በጣም ነው የማዝነው ሰው ሁሉ ለካ የራሱን ቁስል ይዞ ነው የሚዞረው››ስትል አሰበች፡፡
አዎ..ይሄንን ታሪክ የሚያውቁ በጣም የቅርቤ የሆኑ ጥቂት ሰዎች ናቸው..እና ከዛ በኋላ የማሳጅ ስራ እንዴት መስራት እችላለሁ...? ገና የማሳጅ ጠረጴዛው ላይ የሆነ ሴት መጥታ ስትተኛ ፊቴ ድቅን የምትለው እሷ ነች…..ልክ በገዛ እጄ አንቄ እንደገደልኳት ወይም በገመድ አንጠልጥዬ ነፍሷን እንደነጠቅኳት ይታሰበኝና እጄ ሆነ መላ ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል…ከዛ አቃተኝና ይብቃኝ አልኩ…ትብለጥም ከመጀመሪያው ጀምሮ ታሪኩን ታውቅ ስለነበረ ወዲያው ጥያቄዬን ተቀበለችና ይሄንን አሁን የምሰራውን ስራ እንድሰራና ድርጅቱን ልክ እንደቤተሰብ ድርጅት እንዳገለግል ጠየቀችኝ ..እኔም ተቀበልኳት…እና ይሄው ሁለት አመት ድርጅቱ በሚፈልገኝ በማንኛውም ቦታ እየገባሁ ያለውን ስራ ሁሉ እሰራለሁ…በጣም ጥሩ የሚባል ደሞዝም ይከፈለኛል…እና ታሪኩ እንደዛ ነው እልሻለሁ ፡፡
‹‹በጣም ያሳዘናል፡፡››…አለች የእውነትም ከልቧ አዝና…ከመጠጡ ጋር ወደ ውስጧ ያስገባችው አሳዛኝ ታሪክ በሰውነቷ ሙቀት ለቀቀባት…ስትቁነጠነጥ አየና‹‹ ምነው ምን ፈለግሽ?››ሲል ጠየቃት፡
‹‹እኔ እንጃ… ሞቀኝ …ሰውነቴን ለቅለቅ ብል ደስ ይለኛል፡፡››አለችው፡፡
የጠበቀው‹‹መሸ ወደ ሆቴሌ አድርሰኝ›› የምትለው ነበር የመሰለው፡፡ቶሎ ብሎ ተነሳና‹‹ተነሽ ምን ችግር አለው..እንደቤትሸ ቁጠሪው››አለና እየመራ ወደ ውስጠኛው ክፍል ይዟት ሄደ…አንዱን ክፍል ከፍቶ ገባ ተከተለችው፡፡መኝታ ክፍሉ ከሳሎኑ ብዙም የማይተናነስ ሰፊ ክፍል ነው፡፡መሀከል ላይ ነጭ አልጋ ልብስ በስርዓት የተነጠፈበት ነጭ ግዙፍ አልጋ ይታያል…በአንደኛው የግድግዳ ሙሉ ቁም ሳጥን የተገጠመለት ነው፡፡
‹‹ይሄ ሁሉ ቁም ሳጥን ልብስ ካለበት ይገርመኛል››አለች፡፡
ወደ ቁም ሳጥኑ አመራና አንዱን በራፍ ከፍቶ ከተደረደሩት በርካታ አንሶላና ፎጣዎች ውስጥ አንድ ነጭ ፎጣ አወጣና እያቀበላት
‹‹ያው ግቢና ታጠቢ ሳሎን እጠብቅሻለሁ››አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሳምንት ሙሉ ታገስኩ….ላብድ ደረስኩ…ስራ ሁሉ መስራት አቃተኝ….ከ15ቀን በኋላ ሰውዬውን የሆነ ስብሰባ ሲመራ በቲቪ አየሁት….ደስ አለኝ፡፡ልክ እሷን ያገኘሁ ነው የመሰለኝ…..በቃ እሷም መጥታለች ማለት ነው ስል አሰብኩ….ማንንም እንዳታገኝ ቤት ውስጥ ቆልፎባታል ስል በማሰብ እርግጠኛ ወደመሆን ተሸጋገርኩ እሷን ነፃ ለማውጣት ወሰንኩ፡፡ ጓደኞቼን እንዲረዱኝ ጠየቅኩ፡፡ የሰውየውን ቤት ቀንና ሌሊት ማጥናትና መሰለል ጀመርን፤የሚገባውንና የሚወጣውን ሁሉ መከታተል ቀጠልን…በአራተኛው ቀን ቤቱ ያሉት አንድ የቤት ሰራተኛ አንድ ነርስ እና አንድ ህፃን ልጅ ብቻ እንደሆኑ አረጋገጥን›› የምሆነውም የማደርገውም ነገር ግራ ገባኝ…ሰራተኛዋ እቃ ለመግዛት ከቤት ስትወጣ ጠብቀን አገትናትና አስፈራርተን መረጃ ጠየቅናት..ሴትዬዋም ፈርታ ስለነበረ የምታውቀውን ሁሉ ምንም ሳታስቀር ዘረዘረችልን፡፡
‹‹ምን አለቻችሁ ?ምን ሆና ነው?››ሳባ የተፈጠረውን ለማወቅ በጉጉት ጠየቀች፡፡
‹‹ሚስቱ ከአሜሪካ ወደሀገሬ አልመለስም ብላ አንደኛውን ልጅ ይዛበት እንደተሰወረች..ለ15 ቀን ከዛሬ ነገ ተመልሳ ትመጣለች ብሎ ሲጠብቃትና ሲያስፈልጋትም ከቆየ በኋላ ተስፋ ቆርጦ የተወችለትን አንደኛውን ልጁን ይዞ ወደ ሀገር እንደተመለሰ እንደነገራቸው፣…እና ሁልጊዜ ወደቤት ሲገባ እሱን እያሰበ እንደሚያዝንና እንደሚተክዝ ነገረችን….ላምን አልቻልኩም፡፡
በሰማሁት ዜና በጣም ተረበሽኩ..ላብድ ደረስኩ‹‹እሷ በፍፁም እንደዛ አታደርግም..አንደዛ ብታደርግ ኖሮ ቢያንስ ካለችበት ቦታ ለእኔ የሆነ መልዕክት ትልክልኝ ነበር…ኢሜሌንም ሁለቱንም ስልክ ቁጥሬን በቃሏ ልክ እንደገዛ ስሟ ነው የምታውቀው….እና የሆነ ነገር እንደሆነች ገባኝ፡፡ በህይወቴ ወሰንኩና እሷ ምን እንደሆነች ለመረዳት አንድ አደገኛ ነገር ለማድረግ ወሰንኩ በሁለት ቦዲጋርድ እየታጀበ ወደቤቱ የሚመጣውንና የሚሄደውን ሚኒስቴር ዲኤታ በጓደኞቼ እገዛ ቤት ውስጥ ገብቼ በገዛ መኝታ ቤቱ ለመተኛት ሲገባ ጠበቅኩና ሽጉጥ ግንባሩ ላይ ደቅኜ እጆቹንና እግሮቹን ጠፍሬ ከወንበር ጋር አሰርኩትና እውነቱን እንዲነግረኝ ጠየቅኩት››
‹አንተ ነህ ማለት ነው ውሽማዋ?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
‹‹ሚስትህን እንደዛ አይነት ስህተት ውስጥ እንድትገባ የገፋፋሀት አንተው ነህ
…ምንም አይነት ለአሷ የሚሆን ጊዜ አልነበረህም….››አልኩት፡፡
‹‹እና በእኔ ላይ መሸርሞጧ ትክክል ነው ትላለህ?››
‹‹አንተም እኮ ስፍር ቁጥር ከሌላቸው ሴቶች ጋር በየሆቴሉና ሎጁ ስትቀብጥና ስትሸረሙጥ መኖርህን አውቃለሁ…ከፈለክ መረጃው አለኝ….አልኩና ሞባይሌ ላይ ከነበሩት አንድ ሶስት መረጃዎች ውስጥ ከፈትኩና አሳየሁት›
‹‹እና እኔ ስላደረኩት እሷ ማድረግ አለባት እያልክ ነው…?ደግሞ ቢያንስ እኔ እኮ ልጅ ወልጄ አላመጣሁባትም››
‹‹አይ አንተም ንፁህ አይደለህም ስለዚህ ይቅርታ ይገባታል እያልኩህ ነው…አሁን የት ነው የቆለፍክባት?››
‹‹የምን መቆለፍ…ጉዷ ተፍረጥርጦ ሲወጣ እዛው አሜሪካ ነው አንደኛውን ልጇን ይዛ የተሰወረችው›› ብሎ ሊያታልለኝ ሞከረ….ብዙ ሞከርኩ ሲያስቸግረኝ አፉን አፈንኩትና ገልብጬ እግሩ እስኪተለተል ወፌ ላላ ስገርፈው…በመጨረሻ አመነልኝ፡፡ ሲጨቃጨቅ ድንገት እንደመታትና እንደሞተችበት…ከዛ ለአሜሪካ ጋንግስተሮቸ ብዙ ብር ከፍሎ እሬሳዋ እንዲወገድ እንዳደረገ እና የእሱ ያልሆነውን ልጁም ነጥሎ ለማደጎ ድርጅቶች እንደሰጠ አፉን ሞልቶ ነገረኝ….ልጁን የሰጠበትን የማደጎ ድርጅት አድራሻ ተቀበልኩትና ልገድለው ፈለኩ፤ከራሴ ጋር ለበርካታ ደቂቃዎች ተሟገትኩ ግን የልጄ ወንድም አባት ነው…እንዴት ምንም ያማያውቀውን ህፃን ያለእናት መቅረቱ ሳያንስ ያለአባት አስቀረዋለሁ? ብዬ አሰብኩ….፡፡
ከዛ ስለእኔ ለሌላ ሰው ቢያወራ ሊበቀለኝ ሙከራ ቢያደርግ እሱንም አሳልፌ እንደምሰጠው ስልጣኑንም ክብሩንም አጥተን እስር ቤት እንዲበሰብስ እንደማደርገው ነግሬ በገባሁበት ቦታ ጋርዶቹ ሳያዩኝ ጥዬው ወጣሁ፡፡
‹‹እና አላሳሰርከውም?››
‹‹ባሳስረው ምን ይጠቅመኛል…?አራስ ልጅ እኮ አለው...ልጁ ደግሞ ምንም ቢሆን የእሷ ነው››
‹‹ከዛ በኋላ ሊያጠቃህ አልሞከረም?››
‹‹በፍፁም ስሬ ድርሽ አላለም፡፡››
‹‹እና ልጅህን የምታስመልስበት ምንም መንገድ አላገኘህም?.››
አሜሪካ በሚገኙ ወዳጆቼ አማካይነት ለረጅም ጊዜ ካፈላለኩ በኃላ የዛሬ ወር አካባቢ ትክክለኛ አድርሻውን አገኘሁ፡፡››
‹‹በእውነት ደስ ሲል..››
‹አዎ ደስ ይላል.. እሱ ለማደጎ ድርጅት ቢያስረክበውም .ማደጎ ድርጅቱ ደግሞ አሳዳጊ አግኝቶ ለአንድ አሜሪካዊ ጥንዶች አስተላልፈው ስለሰጡት አሁን በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ማወቅ ችያለሁ…..እግዜር ካለ በቅርብ ሄጄ እንደማየውና ከተቻለ ይዤው እንደምመጣ ከልሆነ እንኳን ከወላጆቹ ጋር ተዋውቄ ልጄንም አይቼ መምጣት ፈልጋለሁ..፡፡
‹‹በጣም ነው የማዝነው ሰው ሁሉ ለካ የራሱን ቁስል ይዞ ነው የሚዞረው››ስትል አሰበች፡፡
አዎ..ይሄንን ታሪክ የሚያውቁ በጣም የቅርቤ የሆኑ ጥቂት ሰዎች ናቸው..እና ከዛ በኋላ የማሳጅ ስራ እንዴት መስራት እችላለሁ...? ገና የማሳጅ ጠረጴዛው ላይ የሆነ ሴት መጥታ ስትተኛ ፊቴ ድቅን የምትለው እሷ ነች…..ልክ በገዛ እጄ አንቄ እንደገደልኳት ወይም በገመድ አንጠልጥዬ ነፍሷን እንደነጠቅኳት ይታሰበኝና እጄ ሆነ መላ ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል…ከዛ አቃተኝና ይብቃኝ አልኩ…ትብለጥም ከመጀመሪያው ጀምሮ ታሪኩን ታውቅ ስለነበረ ወዲያው ጥያቄዬን ተቀበለችና ይሄንን አሁን የምሰራውን ስራ እንድሰራና ድርጅቱን ልክ እንደቤተሰብ ድርጅት እንዳገለግል ጠየቀችኝ ..እኔም ተቀበልኳት…እና ይሄው ሁለት አመት ድርጅቱ በሚፈልገኝ በማንኛውም ቦታ እየገባሁ ያለውን ስራ ሁሉ እሰራለሁ…በጣም ጥሩ የሚባል ደሞዝም ይከፈለኛል…እና ታሪኩ እንደዛ ነው እልሻለሁ ፡፡
‹‹በጣም ያሳዘናል፡፡››…አለች የእውነትም ከልቧ አዝና…ከመጠጡ ጋር ወደ ውስጧ ያስገባችው አሳዛኝ ታሪክ በሰውነቷ ሙቀት ለቀቀባት…ስትቁነጠነጥ አየና‹‹ ምነው ምን ፈለግሽ?››ሲል ጠየቃት፡
‹‹እኔ እንጃ… ሞቀኝ …ሰውነቴን ለቅለቅ ብል ደስ ይለኛል፡፡››አለችው፡፡
የጠበቀው‹‹መሸ ወደ ሆቴሌ አድርሰኝ›› የምትለው ነበር የመሰለው፡፡ቶሎ ብሎ ተነሳና‹‹ተነሽ ምን ችግር አለው..እንደቤትሸ ቁጠሪው››አለና እየመራ ወደ ውስጠኛው ክፍል ይዟት ሄደ…አንዱን ክፍል ከፍቶ ገባ ተከተለችው፡፡መኝታ ክፍሉ ከሳሎኑ ብዙም የማይተናነስ ሰፊ ክፍል ነው፡፡መሀከል ላይ ነጭ አልጋ ልብስ በስርዓት የተነጠፈበት ነጭ ግዙፍ አልጋ ይታያል…በአንደኛው የግድግዳ ሙሉ ቁም ሳጥን የተገጠመለት ነው፡፡
‹‹ይሄ ሁሉ ቁም ሳጥን ልብስ ካለበት ይገርመኛል››አለች፡፡
ወደ ቁም ሳጥኑ አመራና አንዱን በራፍ ከፍቶ ከተደረደሩት በርካታ አንሶላና ፎጣዎች ውስጥ አንድ ነጭ ፎጣ አወጣና እያቀበላት
‹‹ያው ግቢና ታጠቢ ሳሎን እጠብቅሻለሁ››አላት፡፡
#ኢትዬጵያዊ_ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ካርሎስና እና ኑሀሚ በአምስተኛ ቀናቸው ነበር ከአከባቢው የተንቀሳቀሱት፡፡በዛን ወቅት ኑሀሚ የተመረዘችው መርዝ ሙሉ በሙሉ ከሰውነቷ ተወግዶ… የሟሸሸ የነበረም ሰውነቷ ተነቃቅቶ….ጥንካሬዋም በተወሰነ ፐርሰንት ተመልሶ ነበረ፡፡ ባለውለታቸውን የሆነችውን ጎጆ በፍቅር ተሰናብተው አካባቢውን ለቀው የአማዞንን ወንዝ ደርቻ ተከትለው በምስራቅ አቅጣጫ ለአንድ ሰዓት ተኩል በእግር ከተጓዙ በኃላ አንድ እሮጌ ጀልባ የያዘ ግለሰብ አጋጠማቸው፡፡ከእሱ ጋር በገንዘብ ተደራደሩና ታብቲንጋ ከተማ ድረስ እንዲያደርሳቸው ተስማምተው ጉዞ ጀመሩ፡፡የዛኑ ቀን አመሻሽ ላይ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡
‹‹ይህቺ ከተማ የአየር ትርንስፓርት አገልግሎት አላት ነው ያልከኝ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ አላት..ማኑሳ ድረስ መሄድ ይቻላል፡፡››
‹‹ታድለን…በቃ ነገሮች ወደመጨረሻው ምዕራፍ እየተቃረበ ነው ማለት ነው…ተዲያ ወደከተማው እንግባና የአየር ትኬት ካገኘን እንሞክራ››
‹‹አይ ወደከታማ መግባት አንችልም..፡፡እንደምታያት ይህቺ አንስተኛ የጠረፍ ከተማ ብራዚል ውስጥ ትገኝ እንጂ ለኮሎምቢያ ቅርብ መሆኗን እንዳትረሺ..ያ ማለት ደግሞ የዳግላስ ተፅእኖ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ይኖራል ማለት ነው፡፡ በተለይ ወደ ብራዚል ከገባን ቀጥታ የአየር ትራንስፖርት የሚገኝባት ከተማ ይህቺ ስለሆነች ቀጥታ ወደእዚህ እንደምንመጣና ወደአየር መረፊያ ጎራ እንደምንል በቀላሉ ይገምታል..ስለሆነም ከተማው ውስጥ ዋና ዋና ቦታዎች እና በተለይ ደግሞ አየር ማረፊያ ላይ ሰዎቹን እንደሚያስቀምጥ እርግጠኛ ነኝ፡፡
‹‹እና ምን ይሻለናል?፡፡››በስጋት ጠየቀችው፡፡
‹‹ረጅሙን መንገድ ነው የምንመረጠው..ማለት አሁንም ወደ ምስራቅ ጉዞችንን እንቀጥልና ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ ነው የምንሄደው፡፡››
‹‹ቤንጃሚን ኮንስተንት ደግሞ ማን ነች?››
ቤንጃሚን ኮንስተንት አማዞን ደን ውስጥ ከበቀሉ የብራዚል የጠረፍ ከተሞች ውስጥ አንዷ ስትሆን ከተማዋ ጃዋሪ በተባለ ወንዝና በአማዞን ወንዝ ተከባ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ነች፡፡ከዚህ አሁን ካለንበት ከተማ በጀልባ የሁለት ሰዓት ቢፈጅብን ነው፡፡ማንም ወደ ዛች ከተማ ይሄዳሉ ብሎ እይገምተንም…እዛ ከደረስን በኃላ የተሻለ የተባለ ዘመናዊ ጀልባ እንከራይና ቀጥታ ወደ ማናአስ እንጓዛለን፡፡
‹እንዳልክ …ግን የሆነ ቻርጅ ያለበት ቦታ ፈልግን ስልኬን ቻርጅ ማድረግ አለብኝ፡››የምታስበውን ነገረችው፡፡
‹‹ምን ሊያደርግልሽ?››
‹‹ትቅዳለህ..ለወንድሜ ደውዬ ቢያንስ እስከሁን በጤና መሆኔን ላሳውቀው ነዋ፡፡››
‹‹አይ አይሆንም…ስልክሽን አብርተሸ ለወንድምሽ ደወልሽለት ማለት ያለሽበትን አካባቢ ቀጥታ ለሀገርሽ መንግስት እናም ጉደዩን ለሚከታተሉ ለአካባቢው መንግስታት አሰወቅሽ ማለት ነው..ያ ሆነ ማለት ደግሞ ዳግላስም በቀላሉ ዜናውን አገኘ ማለት ነው፡፡እና ሁሉም እኛን ለማግኘት በአካባቢው አሰሳ ይጀምራሉ…ከዚህ በፊት እንዳለኝ ልምድ ደግሞ ከየትኛውም መንግስት ቀድሞ ደጋላስ አፈፍ እንደሚያደርገን እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና ምን ይሻላል?››
‹‹የሚሻለውማ..ማናስ እስክንገባ መቻል….ነው…ወንድምሽም ዘላለም ከሚያጣሽ…ስድስት ሰባት ቀን በናፍቆት እና በትካዜ ቢሰቃይ ይሻላል፡፡አሁን አንቺ እዚሁ አካባቢ እራስሽን ከሰው እይታ ከልለሽ ትጠብቂኛለሽ… እኔ እራሴን ለውጬ ከታማ ገብቼ እመለሳለሁ››
‹‹እንዴ… እኔን እዚህ ብቻዬን ጥለኸኝ ምን ትሰረለህ?››
እጁን ወደኪሱ ሰደደና የሆነ መሀረብ አውጥቶ ቋጠሮውን ፈታና ሁለት የጨው አንኳር የሚመስል አብረቅራቀ መአድን አነሳና በእጇ መዳፍ ላይ አስቀመጠ፡
‹‹ምንድነው?››በመገረም እያየች ጠየቀችው፡፡
‹‹እንቁ ነው..በደኑ ውስጥ በአጋጣሚ በስራ ላይ እያለው በእጄ የገባ ነው..እንደዚህ አይነት ንብረት በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆንም በእጅ ከገባ ለገዛ ጥቅም ደብቆ መስቀመጥ በሞት የሚያስቀጣ አደገኛ ወንጀል ነው..በወቅቱ ለዳግላስ ማሰረከብ ነበረብኝ…እኔ ግን ደመነፍሴ አንድ ቀን አጣብቂኝ ውስጥ ስገባ ይጠቅምሀል ብሎ ሹክ ስላለኝ..የመጣው ይምጣ ብዬ ደብቄ አስቀምጬው ነበር፣.እና አሁን ወደከተማ ሄጄ ወደገንዘብ ልቀይረው...እረጅም የጀልባ ጉዘ ስለሚጠብቅ ብዙ ገንዘብ ያሰፈልገናል…››
መጀመሪያ እንቁውን መለሰችለት..መልሶ በመሀረቡ ቋጠረውና ወደኪሱ ከተተው..፡፡
ከሷ የእጅ ቦርሳዋን አነሰችና ዚፕን ከፈተች፣ከላይ ያሉትን እቃዎች አወጣች ፡፡ፊቱን አዙሮ ሊሄድ ሲል ከስር እንደታሸገ የተቀመጠውን ዶለር መዥርጣ አወጣችና እጁ ላይ አስቀመጠችለት፡፡
‹‹ይሄ አይበቃም?››
አይኖቹ በመገረም ደመቁ‹‹አንቺ ይሄን ሁሉ ብር ከየት አመጣሽ?››
የዛሬን አያድርገውና ሀለቃህ ዳግስ ነበር የሰጠኝ..እና አይበቃም›››….ብላ እንዴት እንዳገኘች ታሪኩን አስረዳችው
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..ይሄ እኮ በጣም ብዙ ብር ነው….በይ አሁን ጀልበ እንፈልግ››አለና ብሩን መልሶላት ቦርሳ ውስጥ ከከተተ በኃላ ተያይዘው ወደፊት ለፊት መራመድ ጀመሩ፡፡
እንደተነጋገሩት እዛው አድረው ንጊት ላይ ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ በጅልባ ተጓዙ፡፡ እዛ አንድ ሰዓት ብቻ በማሳለፍ ሌላ ዘመናዊ የተባለ ጀልባ ተከራዩና ወደአማዞኒያ ግዛት ዋና ከተማ ማናአስ ጉዞ ጀመሩ፡.ያው ጉዞ ቀላል አልነበረም….6 ቀን ነው የፈጀባቸው ፡፡ግን ደግሞ በህይወት ረጅም ዘመን ለመኖር ስድስትና ሰባት ቀን መስዋት ማድረግ ያን ያህል ክፉ የሚባል ስላልሆነ አላማረረችም ፡፡
…ታብቲንጋ….ሳኦ ፍረንሲስኮ…ኮረንቲዛ….ዲ አማተራ…ሳኦ ዶሚንጎ….ሳንታ አንቶኒኦ….ሳኦ ፍሊክስ… ሳንታ ሉዚያ… የመሳሰሉን አያሌ ታዋቂ ቦታዎችንና የኣማዞን ወንዝ ዳር ከተሞችን አቋርጠው ማናአስ ከተማ ደረሱ ፡፡
ማናአስ(Manaus) በሀገረ ብራዚል የኣማዞኑያ ግዛት ዋና ከተማ ነች፡፡በብራዚል 2.2 ሚሊዬን ኑዋሪዎች የሚኖሩበት 7ተኛው ትልቋ ከተማ ስትሆን ከተማዋ በአማዞን ደን ውስጥ ከተቆረቆሩ ከ1 ሚሊዬን በላይ ኑዋሪዎች ካሏቸው ሁለት ትልልቅ ከተሞች መካከል አንዶ እና ዋነኛዋ ነች.››
በዛ ላይ የአማዞን ደንን እና የአማዞን ወንዝን ሚስጥር ለመበርበር እና ጥናት ለማጥናት ከመላው አለም የሚሰባበሰቡ ሳይንተስቶችና ተመራማሪዎች በዋናነት የሚከትሙባት ከተማ ነች፡፡በዚህ የተነሳ የአማዞን ልብ የሚል ቅፅል ስም ይሰጧታል፡፡በተጨማሪ አንዳንዶችም የትርፒካሎ ፓሪስም እያሉ ያሞካሻታል፡፡
ማናአስ ከተማና አካባቢው በኬሚካል ፕሮጀክት..በለውዝ ምርት ….በሳሙና ምርት….በመርከብ ግንባታ እና በጎማ ተክል ምርት በጣም የታወቀች ነች፡፡፡በተለይ በጎማ ምርት ከ1800 አመት በፈት ጀምሮ የታወቀች በመሆኗ ከሀገሪቱ ሀብታም ከተሞች ግንባር ቀደሞ እንድትሆን አስችሏታል፡፡ማናአስ ከተማ በ2014 እ.ኤ.አ የአለምን ዋንጫ ካስተናገዱ 12 የብራዚል ከተሞች አንዷ እንደሆነች ይታወቃል፡፡በከተማዋ ምስራቅ አቅጣጫ ድፍርሱ የኒግሮ ወንዝ እና ሰማያዊው የሶሊመስ ወንዝ አንድ ላይ ተቀላለቅሎ ወደአማዞን በገባርነት የሚፈስባት ልዩና አስደማሚ ስፍራንም በመደመም ማየት ይቻላል፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ካርሎስና እና ኑሀሚ በአምስተኛ ቀናቸው ነበር ከአከባቢው የተንቀሳቀሱት፡፡በዛን ወቅት ኑሀሚ የተመረዘችው መርዝ ሙሉ በሙሉ ከሰውነቷ ተወግዶ… የሟሸሸ የነበረም ሰውነቷ ተነቃቅቶ….ጥንካሬዋም በተወሰነ ፐርሰንት ተመልሶ ነበረ፡፡ ባለውለታቸውን የሆነችውን ጎጆ በፍቅር ተሰናብተው አካባቢውን ለቀው የአማዞንን ወንዝ ደርቻ ተከትለው በምስራቅ አቅጣጫ ለአንድ ሰዓት ተኩል በእግር ከተጓዙ በኃላ አንድ እሮጌ ጀልባ የያዘ ግለሰብ አጋጠማቸው፡፡ከእሱ ጋር በገንዘብ ተደራደሩና ታብቲንጋ ከተማ ድረስ እንዲያደርሳቸው ተስማምተው ጉዞ ጀመሩ፡፡የዛኑ ቀን አመሻሽ ላይ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡
‹‹ይህቺ ከተማ የአየር ትርንስፓርት አገልግሎት አላት ነው ያልከኝ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ አላት..ማኑሳ ድረስ መሄድ ይቻላል፡፡››
‹‹ታድለን…በቃ ነገሮች ወደመጨረሻው ምዕራፍ እየተቃረበ ነው ማለት ነው…ተዲያ ወደከተማው እንግባና የአየር ትኬት ካገኘን እንሞክራ››
‹‹አይ ወደከታማ መግባት አንችልም..፡፡እንደምታያት ይህቺ አንስተኛ የጠረፍ ከተማ ብራዚል ውስጥ ትገኝ እንጂ ለኮሎምቢያ ቅርብ መሆኗን እንዳትረሺ..ያ ማለት ደግሞ የዳግላስ ተፅእኖ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ይኖራል ማለት ነው፡፡ በተለይ ወደ ብራዚል ከገባን ቀጥታ የአየር ትራንስፖርት የሚገኝባት ከተማ ይህቺ ስለሆነች ቀጥታ ወደእዚህ እንደምንመጣና ወደአየር መረፊያ ጎራ እንደምንል በቀላሉ ይገምታል..ስለሆነም ከተማው ውስጥ ዋና ዋና ቦታዎች እና በተለይ ደግሞ አየር ማረፊያ ላይ ሰዎቹን እንደሚያስቀምጥ እርግጠኛ ነኝ፡፡
‹‹እና ምን ይሻለናል?፡፡››በስጋት ጠየቀችው፡፡
‹‹ረጅሙን መንገድ ነው የምንመረጠው..ማለት አሁንም ወደ ምስራቅ ጉዞችንን እንቀጥልና ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ ነው የምንሄደው፡፡››
‹‹ቤንጃሚን ኮንስተንት ደግሞ ማን ነች?››
ቤንጃሚን ኮንስተንት አማዞን ደን ውስጥ ከበቀሉ የብራዚል የጠረፍ ከተሞች ውስጥ አንዷ ስትሆን ከተማዋ ጃዋሪ በተባለ ወንዝና በአማዞን ወንዝ ተከባ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ነች፡፡ከዚህ አሁን ካለንበት ከተማ በጀልባ የሁለት ሰዓት ቢፈጅብን ነው፡፡ማንም ወደ ዛች ከተማ ይሄዳሉ ብሎ እይገምተንም…እዛ ከደረስን በኃላ የተሻለ የተባለ ዘመናዊ ጀልባ እንከራይና ቀጥታ ወደ ማናአስ እንጓዛለን፡፡
‹እንዳልክ …ግን የሆነ ቻርጅ ያለበት ቦታ ፈልግን ስልኬን ቻርጅ ማድረግ አለብኝ፡››የምታስበውን ነገረችው፡፡
‹‹ምን ሊያደርግልሽ?››
‹‹ትቅዳለህ..ለወንድሜ ደውዬ ቢያንስ እስከሁን በጤና መሆኔን ላሳውቀው ነዋ፡፡››
‹‹አይ አይሆንም…ስልክሽን አብርተሸ ለወንድምሽ ደወልሽለት ማለት ያለሽበትን አካባቢ ቀጥታ ለሀገርሽ መንግስት እናም ጉደዩን ለሚከታተሉ ለአካባቢው መንግስታት አሰወቅሽ ማለት ነው..ያ ሆነ ማለት ደግሞ ዳግላስም በቀላሉ ዜናውን አገኘ ማለት ነው፡፡እና ሁሉም እኛን ለማግኘት በአካባቢው አሰሳ ይጀምራሉ…ከዚህ በፊት እንዳለኝ ልምድ ደግሞ ከየትኛውም መንግስት ቀድሞ ደጋላስ አፈፍ እንደሚያደርገን እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና ምን ይሻላል?››
‹‹የሚሻለውማ..ማናስ እስክንገባ መቻል….ነው…ወንድምሽም ዘላለም ከሚያጣሽ…ስድስት ሰባት ቀን በናፍቆት እና በትካዜ ቢሰቃይ ይሻላል፡፡አሁን አንቺ እዚሁ አካባቢ እራስሽን ከሰው እይታ ከልለሽ ትጠብቂኛለሽ… እኔ እራሴን ለውጬ ከታማ ገብቼ እመለሳለሁ››
‹‹እንዴ… እኔን እዚህ ብቻዬን ጥለኸኝ ምን ትሰረለህ?››
እጁን ወደኪሱ ሰደደና የሆነ መሀረብ አውጥቶ ቋጠሮውን ፈታና ሁለት የጨው አንኳር የሚመስል አብረቅራቀ መአድን አነሳና በእጇ መዳፍ ላይ አስቀመጠ፡
‹‹ምንድነው?››በመገረም እያየች ጠየቀችው፡፡
‹‹እንቁ ነው..በደኑ ውስጥ በአጋጣሚ በስራ ላይ እያለው በእጄ የገባ ነው..እንደዚህ አይነት ንብረት በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆንም በእጅ ከገባ ለገዛ ጥቅም ደብቆ መስቀመጥ በሞት የሚያስቀጣ አደገኛ ወንጀል ነው..በወቅቱ ለዳግላስ ማሰረከብ ነበረብኝ…እኔ ግን ደመነፍሴ አንድ ቀን አጣብቂኝ ውስጥ ስገባ ይጠቅምሀል ብሎ ሹክ ስላለኝ..የመጣው ይምጣ ብዬ ደብቄ አስቀምጬው ነበር፣.እና አሁን ወደከተማ ሄጄ ወደገንዘብ ልቀይረው...እረጅም የጀልባ ጉዘ ስለሚጠብቅ ብዙ ገንዘብ ያሰፈልገናል…››
መጀመሪያ እንቁውን መለሰችለት..መልሶ በመሀረቡ ቋጠረውና ወደኪሱ ከተተው..፡፡
ከሷ የእጅ ቦርሳዋን አነሰችና ዚፕን ከፈተች፣ከላይ ያሉትን እቃዎች አወጣች ፡፡ፊቱን አዙሮ ሊሄድ ሲል ከስር እንደታሸገ የተቀመጠውን ዶለር መዥርጣ አወጣችና እጁ ላይ አስቀመጠችለት፡፡
‹‹ይሄ አይበቃም?››
አይኖቹ በመገረም ደመቁ‹‹አንቺ ይሄን ሁሉ ብር ከየት አመጣሽ?››
የዛሬን አያድርገውና ሀለቃህ ዳግስ ነበር የሰጠኝ..እና አይበቃም›››….ብላ እንዴት እንዳገኘች ታሪኩን አስረዳችው
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..ይሄ እኮ በጣም ብዙ ብር ነው….በይ አሁን ጀልበ እንፈልግ››አለና ብሩን መልሶላት ቦርሳ ውስጥ ከከተተ በኃላ ተያይዘው ወደፊት ለፊት መራመድ ጀመሩ፡፡
እንደተነጋገሩት እዛው አድረው ንጊት ላይ ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ በጅልባ ተጓዙ፡፡ እዛ አንድ ሰዓት ብቻ በማሳለፍ ሌላ ዘመናዊ የተባለ ጀልባ ተከራዩና ወደአማዞኒያ ግዛት ዋና ከተማ ማናአስ ጉዞ ጀመሩ፡.ያው ጉዞ ቀላል አልነበረም….6 ቀን ነው የፈጀባቸው ፡፡ግን ደግሞ በህይወት ረጅም ዘመን ለመኖር ስድስትና ሰባት ቀን መስዋት ማድረግ ያን ያህል ክፉ የሚባል ስላልሆነ አላማረረችም ፡፡
…ታብቲንጋ….ሳኦ ፍረንሲስኮ…ኮረንቲዛ….ዲ አማተራ…ሳኦ ዶሚንጎ….ሳንታ አንቶኒኦ….ሳኦ ፍሊክስ… ሳንታ ሉዚያ… የመሳሰሉን አያሌ ታዋቂ ቦታዎችንና የኣማዞን ወንዝ ዳር ከተሞችን አቋርጠው ማናአስ ከተማ ደረሱ ፡፡
ማናአስ(Manaus) በሀገረ ብራዚል የኣማዞኑያ ግዛት ዋና ከተማ ነች፡፡በብራዚል 2.2 ሚሊዬን ኑዋሪዎች የሚኖሩበት 7ተኛው ትልቋ ከተማ ስትሆን ከተማዋ በአማዞን ደን ውስጥ ከተቆረቆሩ ከ1 ሚሊዬን በላይ ኑዋሪዎች ካሏቸው ሁለት ትልልቅ ከተሞች መካከል አንዶ እና ዋነኛዋ ነች.››
በዛ ላይ የአማዞን ደንን እና የአማዞን ወንዝን ሚስጥር ለመበርበር እና ጥናት ለማጥናት ከመላው አለም የሚሰባበሰቡ ሳይንተስቶችና ተመራማሪዎች በዋናነት የሚከትሙባት ከተማ ነች፡፡በዚህ የተነሳ የአማዞን ልብ የሚል ቅፅል ስም ይሰጧታል፡፡በተጨማሪ አንዳንዶችም የትርፒካሎ ፓሪስም እያሉ ያሞካሻታል፡፡
ማናአስ ከተማና አካባቢው በኬሚካል ፕሮጀክት..በለውዝ ምርት ….በሳሙና ምርት….በመርከብ ግንባታ እና በጎማ ተክል ምርት በጣም የታወቀች ነች፡፡፡በተለይ በጎማ ምርት ከ1800 አመት በፈት ጀምሮ የታወቀች በመሆኗ ከሀገሪቱ ሀብታም ከተሞች ግንባር ቀደሞ እንድትሆን አስችሏታል፡፡ማናአስ ከተማ በ2014 እ.ኤ.አ የአለምን ዋንጫ ካስተናገዱ 12 የብራዚል ከተሞች አንዷ እንደሆነች ይታወቃል፡፡በከተማዋ ምስራቅ አቅጣጫ ድፍርሱ የኒግሮ ወንዝ እና ሰማያዊው የሶሊመስ ወንዝ አንድ ላይ ተቀላለቅሎ ወደአማዞን በገባርነት የሚፈስባት ልዩና አስደማሚ ስፍራንም በመደመም ማየት ይቻላል፡፡
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ _ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ባልና ሚስቶቹን ቤታቸው ወስዶ እንደጣላቸው ቀጥታ የመኪናውን መሪ ወደአስቴር ቢሮ ነው የጠመዘዘው…ገብቶ ምሳ እንዲበላ ቢለምኑት እንኳን እሺ አላለቸውም፡፡እንደሚመጣ አልነገራትም ቀጥታ ከቢሮዋ ፊት ለፊት አቆመና ደወለ
‹‹ሄሎ ወንድሜ….እንዴት ነው ቢሾፍቱ በጣም ተመችታሀለች መሰለኝ?፡፡››
‹‹መጥቻለው….ምሳ አትጋብዢኝም?፡፡››
‹‹የእውነት መጣህ?››
‹‹አዎ ቢሮሽ ፊት ፊት መኪናዬን አቁሜያለው፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ››ብላ ስልኩን ዘጋች….5 ደቂቃ ነው ያስጠበቀችው፡፡ገና የቢሮዋን የህንፃ ደረጃ ስትወርድ ጀምሮ ነው አይኑ ውስጥ የገባችው…ሙሉ ሮዝ ቀለም ያለው ጉረድ ቀሚስና ኮት ለብሳለች…ፀጉሯ ወደኃላዋ ትከሻዋ ላይ እንዲተኛ ተደርጎል…ውብ ሆናለች….መኪናዋን ስለምታውቃት ብዙም ሳትደነጋገር ቀጥታ ወደእሱ ነው ያመራችው…ይህቺ ሴት እህቱ እንድትሆን አይደለም የሚፈልገው…ጓደኛም እንድትሆነው አይደለም…የፍቅር አጋሩ ሚስቱ ሊያደርጋት ነው ምኞቱ..ይሄ ምኞቱ ደግሞ አሁን በቅርብ በውስጡ የበቀለ ስላልሆነ ህመሙ ቀላል አይደለም…ገና አፍ ፈቶ በኮልታፋ አንደበት መንተባተብ በጀመረበት በጮርቃነት እድሜው ጀመሮ እሷ ሚስቱ እንደሆነች ያስብ ነበር፣እርግጥ በዛን እድሜ ሚስት ማለት እራሱ ትርጉሙ ምን ማለት አንደሆነ አያውቅም ነበር፣ቢሆንም ጭላንጭል የሆነ ግንዛቤ ነበረው…ሚስት ማለት አንድ ክፍል ውስጥ አንድ አልጋ ላይ ሁሌ አብራ
የምትተኛ ሴት እንደሆነች ከአባትና ከእናቱ ግንኙነት መረዳት በቻለበት ጊዜ ነው፣ከእሱ ጋር ለዘላለም መተኛት ያለባት ሴት አስቴር እንደሆነች ወስኖ የነበረው፣በዛን የልጅነት ጊዜ እናቷ የቤታቸውን እንጀራ ልትጋግር ስትመጣ አስከትላት ስትመጣ ጀምሮ እዛው እሷን ማስቀረት ምኞቱ ነበር…እና ያ ምኞት ግለቱን ጠብቆ እየፋመ ነበር የቀጠለው…
ጊዜው ሲደርስ ግን ነገሮች ቀደም ብሎ እንዳሰባቸው ቀላል አልነበሩም…ገቢናውን ከፈተላት ገባች.. ጉንጩን አገላብጣ ሳመችው…ሁል ጊዜ የእሷ መሳም ከሌላው መሳም በጣም ይለይበታል…ወፈር ብሎ ወደፊት ግልብጥ ያለው ፍም ከንፈሯ ሰውነቱ ላይ ሲርፍ የተለየ ሙቀት ነው ሰውነቱ የሚያመነጨው…ልክ የጋለ ቢላዋ አካል ላይ ሲያርፍ የሚሰማው አይነት ትሽሽሽ..የሚል የማቃጠል የመለብለብና የመላጠ ስሜት……
‹‹አንተ ወፍረህ ነው የመጣሀው….ስራ ላይ ነበርክ ወይስ ጫጉላ ሽርሽር ላይ?››
‹‹በይው…አንቺም ተመችቶሻል…ምሳ የት አንብላ?››
‹‹ወደ እኔ ቤት ንዳው››
‹‹ምነው ከሰዓት ስራ የለሽም እንዴ?››
‹‹ዛሬ ቅዳሜ እኮ ነው…ግማሽ ቀን ነው የምንሰራው››
‹‹እና አራበሽም ..በልተን ብንሄድ አይሻልም?››
‹‹አይ ሰራተኛዬ አዘጋጅታ እየጠበቀችን ነው…ዘና ብለን ቤታችን ብንበላ ይሻላል….ወንድሜ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል››
‹‹እኔም ከሰዓት ስራ ስለሌለሽ ደስ ብሎኛል››ብሎ መኪናዋን ወደ አስፓልት መሀል አስገባና ነዳት….የእውነትም ከሰዓት ስራ የለኝም ብላ ወደቤቷ ይዛው እየሄደች በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ ተስምቶታል…ከአመታት በኃላ መልሶ ዛሬ እድሉን ይሞክራል፡፡አዎ በስደት ከሄደበት ባእድ ሀገር ተመልሶ የመጣውም ለዚሁ ነው፡፡ከባሎ እንደተለያየችና እሱም በዛ ንዴት ከሀገር ውጭ መሰደዱን ሲሰማ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ የመጣው…አንሆ ተመልሶ በመጣበት ባለፉት ስድስት ወሮች እሷን ከገባችበት ድባቴ እንድትወጣና ያልተሳካ ትዳሯ ከፈጠረባትን የስነልቦና መሰበር እንድታገግም እንደወንድም እንደ ጓደኛም ከዛም አልፎ እንደባለሞያም ከጎኗ ሆኖ ሲያግዛትና ሲደግፋት ነበር…አሁን ግን ልቧ ሌላ ፍቅር
ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ብሎ ያስባል..በዛ ላይ የእሱ እና የእሷ ፍቅር አዲስ ዛሬ የበቀላ ሳይሆን ድሮ በየሁለቱም ልብ ተዳፍኖ ያለ ነው…አሁን ያንን መቆስቆስና መልሶ እንዲቀጣጠል ትንሽ የፍቅር ቤንዚል ማርከፍከፍ ነው…ለዚህ ድርጊት ያበረታታው ሰሞኑን ያየው በአቶ ሃይለልኡል እና በወ.ሮ ስንዱ መካከል የተከሰተው የፍቅር ግርሻ ነው፡፡
‹‹አዎ…አስቴርን አገባታለሁ…ከበፊት ባሏ የወለደችውን አንድ ልጅም እንደልጄ አድርጌ አሳድገዋለው››በውስጡ አልጎመጎመ…‹‹እና በቅርብ ቀን እሷም ወንድሜ የምትለውን ጥሪ ትተውና ባሌ ብላ ትጠራኛለች…ልጇም አጎቴ ብሎ የሚጠራውን አቁሞ አባቴ እንዲለኝ
አደርጋለው››ይሄንን ስላሰበ ብቻ ውስጡ በደስታ ተፍነከነከ..ቤት ሲደርሱ እውነትም እንዳለችው ቆንጆ ምሳ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው፡፡እየተጎራረሱ በሉ፡፡ከምግብ በኃላ ብና ተፈላላቸው..እሷ ሁለት ሲኒ እሱ አንድ ሲና ጠጡና ተጠናቀቀ፡፡
‹‹እዚሁ ልንገራት ወይስ ይዣት ወጣ ልበልና ዘና ያለ ቦታ ወስጄ ዘና ባለ ስሜት ላይ ከሆነች በኃላ ልንገራት ››እያለ ሲወዛገብ ቆየና‹‹እ…ፕሮግራማችን እንዴት ነው….?ወጣ እንበል ወይስ እዚሁ ነው የምንቆየው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ…ወጣ እንላለን..ሱፐርማርኬት ወጥቼ መሸማመት አለብኝ..መጠነኛ ድግስ ደግሳለው፣ማታ እንግዳ አለብኝ››
ንግግሯ ግራ አጋባውም.. ደነገጠም፡፡
‹‹የማታ እንግዳ ምን አይነት ነው?›› our
‹‹አንተም አለህበት…ዛሬ እዚህ ነው አይደል የምታድረው?››
እሷ ጋር እንዲያድር ስለጠየቀችው ደስ ብሏታል ..ግን እንግዳውስ…?ለመሆኑ ማን ነው
…?ሴት ነው ወንድ?፡፡‹‹እሺ ..እዚህ ነው የማድረው…ግን እንግዳውስ?››
‹‹እንግዲህ እሱን ከመጣ በኃላ ነው የምናውቀው…ልደር ካለ ግን እምቢ ማደር አትችልም የምለው አይነት ሰው አይደለም››በማለት ግራ አጋቢ መልስ ሰጠችው፡፡መልሷ ይብልጥ ቁርጠት ለቀቀበት…ይሄኔ ከመስሪያ ቤቷ ባለደረቦች አንዱ ነው….ሀለቃዋ ይሆን እንዴ…?ቢሆንስ ልደር ስላለ እንዴት እሺ ልትለው ትችላለች..?››ወይ ሴቶች ምን አይነት ቅኔ የሆኑ ፍጡሮች እንደሆኑ ሁሌ እንደደነቀው ነው፡፡ወንድም ሴትም በአንድ ላይ ሰው ተብሎ
መፈረጁ አግባብ አይደለም….አስተሳሰባችን እምነትና ፍላጎታችን ምኑም እኮ አይገናኝም››ሲል በውስጡ አብሰለሰለና..ነገሮች እስኪደርሱ ጠብቆ ለማየት ወሰነ…
‹‹ከዛ በፊ የተመቻቸ ጊዜ ካገኘው ነግራታለሁ…እንደውም ከማታው ፕሮግራሞ በፊት የእኔን ሀሳብ መስማት አለባት››የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ‹‹በቃ እንሂዳ››አላት፡፡
‹‹እሺ፣ተነስ ብላ ቦርሳዋን አንጠለጠለችና ተነሳች..ተያይዘው ወጡ ..ያለችው ሱፐር ማርኬት ይዛው ከገባች በኃላ ምትፈልገውን ነገሮች ሁሉ ተገዝተው በመኪናው ከተጫኑ በኃላ.. ማኪያቶ እንጠጣ ብሎ አንድ ፀጥተኛ ካፌ ይዞት ገባና..ፊት ለፊት እንደተቀመጡ እንደምንም እራሱን አጠንክሮ ወደነጥብ መንደርደር ጀመረ
‹‹ለምን ወደውጭ እንደሄድኩ ታውቂያለሽ አይደል?››
‹‹ሁለተኛ ዲግሪህን ለመማር ነዋ››
‹‹አይ ያማ ሽፋን ነው….እውነተኛ ምክንያቴን አንቺም በደንብ ታውቂዋለሽ..ወደውጭ የሄድኩት ባንቺ ተበሳጭቼ ነው፡፡››
‹‹አንተን ለማበሳጨት ብዬ ግን ምንም ያደረኩት ነገር የለም››
‹‹እሱን ማግባት አልነበረብሽም››
‹‹ለምን …ታዲያ አንተን ወንድሜን ማግባት ነበረብኝ?››
‹‹ምን ችግር አለው?እርግጥ እንደወንድምና እህት አንድቤት አድገናል..ግን የስጋ ትስስር አልነበረንም››
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ _ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ባልና ሚስቶቹን ቤታቸው ወስዶ እንደጣላቸው ቀጥታ የመኪናውን መሪ ወደአስቴር ቢሮ ነው የጠመዘዘው…ገብቶ ምሳ እንዲበላ ቢለምኑት እንኳን እሺ አላለቸውም፡፡እንደሚመጣ አልነገራትም ቀጥታ ከቢሮዋ ፊት ለፊት አቆመና ደወለ
‹‹ሄሎ ወንድሜ….እንዴት ነው ቢሾፍቱ በጣም ተመችታሀለች መሰለኝ?፡፡››
‹‹መጥቻለው….ምሳ አትጋብዢኝም?፡፡››
‹‹የእውነት መጣህ?››
‹‹አዎ ቢሮሽ ፊት ፊት መኪናዬን አቁሜያለው፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ››ብላ ስልኩን ዘጋች….5 ደቂቃ ነው ያስጠበቀችው፡፡ገና የቢሮዋን የህንፃ ደረጃ ስትወርድ ጀምሮ ነው አይኑ ውስጥ የገባችው…ሙሉ ሮዝ ቀለም ያለው ጉረድ ቀሚስና ኮት ለብሳለች…ፀጉሯ ወደኃላዋ ትከሻዋ ላይ እንዲተኛ ተደርጎል…ውብ ሆናለች….መኪናዋን ስለምታውቃት ብዙም ሳትደነጋገር ቀጥታ ወደእሱ ነው ያመራችው…ይህቺ ሴት እህቱ እንድትሆን አይደለም የሚፈልገው…ጓደኛም እንድትሆነው አይደለም…የፍቅር አጋሩ ሚስቱ ሊያደርጋት ነው ምኞቱ..ይሄ ምኞቱ ደግሞ አሁን በቅርብ በውስጡ የበቀለ ስላልሆነ ህመሙ ቀላል አይደለም…ገና አፍ ፈቶ በኮልታፋ አንደበት መንተባተብ በጀመረበት በጮርቃነት እድሜው ጀመሮ እሷ ሚስቱ እንደሆነች ያስብ ነበር፣እርግጥ በዛን እድሜ ሚስት ማለት እራሱ ትርጉሙ ምን ማለት አንደሆነ አያውቅም ነበር፣ቢሆንም ጭላንጭል የሆነ ግንዛቤ ነበረው…ሚስት ማለት አንድ ክፍል ውስጥ አንድ አልጋ ላይ ሁሌ አብራ
የምትተኛ ሴት እንደሆነች ከአባትና ከእናቱ ግንኙነት መረዳት በቻለበት ጊዜ ነው፣ከእሱ ጋር ለዘላለም መተኛት ያለባት ሴት አስቴር እንደሆነች ወስኖ የነበረው፣በዛን የልጅነት ጊዜ እናቷ የቤታቸውን እንጀራ ልትጋግር ስትመጣ አስከትላት ስትመጣ ጀምሮ እዛው እሷን ማስቀረት ምኞቱ ነበር…እና ያ ምኞት ግለቱን ጠብቆ እየፋመ ነበር የቀጠለው…
ጊዜው ሲደርስ ግን ነገሮች ቀደም ብሎ እንዳሰባቸው ቀላል አልነበሩም…ገቢናውን ከፈተላት ገባች.. ጉንጩን አገላብጣ ሳመችው…ሁል ጊዜ የእሷ መሳም ከሌላው መሳም በጣም ይለይበታል…ወፈር ብሎ ወደፊት ግልብጥ ያለው ፍም ከንፈሯ ሰውነቱ ላይ ሲርፍ የተለየ ሙቀት ነው ሰውነቱ የሚያመነጨው…ልክ የጋለ ቢላዋ አካል ላይ ሲያርፍ የሚሰማው አይነት ትሽሽሽ..የሚል የማቃጠል የመለብለብና የመላጠ ስሜት……
‹‹አንተ ወፍረህ ነው የመጣሀው….ስራ ላይ ነበርክ ወይስ ጫጉላ ሽርሽር ላይ?››
‹‹በይው…አንቺም ተመችቶሻል…ምሳ የት አንብላ?››
‹‹ወደ እኔ ቤት ንዳው››
‹‹ምነው ከሰዓት ስራ የለሽም እንዴ?››
‹‹ዛሬ ቅዳሜ እኮ ነው…ግማሽ ቀን ነው የምንሰራው››
‹‹እና አራበሽም ..በልተን ብንሄድ አይሻልም?››
‹‹አይ ሰራተኛዬ አዘጋጅታ እየጠበቀችን ነው…ዘና ብለን ቤታችን ብንበላ ይሻላል….ወንድሜ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል››
‹‹እኔም ከሰዓት ስራ ስለሌለሽ ደስ ብሎኛል››ብሎ መኪናዋን ወደ አስፓልት መሀል አስገባና ነዳት….የእውነትም ከሰዓት ስራ የለኝም ብላ ወደቤቷ ይዛው እየሄደች በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ ተስምቶታል…ከአመታት በኃላ መልሶ ዛሬ እድሉን ይሞክራል፡፡አዎ በስደት ከሄደበት ባእድ ሀገር ተመልሶ የመጣውም ለዚሁ ነው፡፡ከባሎ እንደተለያየችና እሱም በዛ ንዴት ከሀገር ውጭ መሰደዱን ሲሰማ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ የመጣው…አንሆ ተመልሶ በመጣበት ባለፉት ስድስት ወሮች እሷን ከገባችበት ድባቴ እንድትወጣና ያልተሳካ ትዳሯ ከፈጠረባትን የስነልቦና መሰበር እንድታገግም እንደወንድም እንደ ጓደኛም ከዛም አልፎ እንደባለሞያም ከጎኗ ሆኖ ሲያግዛትና ሲደግፋት ነበር…አሁን ግን ልቧ ሌላ ፍቅር
ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ብሎ ያስባል..በዛ ላይ የእሱ እና የእሷ ፍቅር አዲስ ዛሬ የበቀላ ሳይሆን ድሮ በየሁለቱም ልብ ተዳፍኖ ያለ ነው…አሁን ያንን መቆስቆስና መልሶ እንዲቀጣጠል ትንሽ የፍቅር ቤንዚል ማርከፍከፍ ነው…ለዚህ ድርጊት ያበረታታው ሰሞኑን ያየው በአቶ ሃይለልኡል እና በወ.ሮ ስንዱ መካከል የተከሰተው የፍቅር ግርሻ ነው፡፡
‹‹አዎ…አስቴርን አገባታለሁ…ከበፊት ባሏ የወለደችውን አንድ ልጅም እንደልጄ አድርጌ አሳድገዋለው››በውስጡ አልጎመጎመ…‹‹እና በቅርብ ቀን እሷም ወንድሜ የምትለውን ጥሪ ትተውና ባሌ ብላ ትጠራኛለች…ልጇም አጎቴ ብሎ የሚጠራውን አቁሞ አባቴ እንዲለኝ
አደርጋለው››ይሄንን ስላሰበ ብቻ ውስጡ በደስታ ተፍነከነከ..ቤት ሲደርሱ እውነትም እንዳለችው ቆንጆ ምሳ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው፡፡እየተጎራረሱ በሉ፡፡ከምግብ በኃላ ብና ተፈላላቸው..እሷ ሁለት ሲኒ እሱ አንድ ሲና ጠጡና ተጠናቀቀ፡፡
‹‹እዚሁ ልንገራት ወይስ ይዣት ወጣ ልበልና ዘና ያለ ቦታ ወስጄ ዘና ባለ ስሜት ላይ ከሆነች በኃላ ልንገራት ››እያለ ሲወዛገብ ቆየና‹‹እ…ፕሮግራማችን እንዴት ነው….?ወጣ እንበል ወይስ እዚሁ ነው የምንቆየው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ…ወጣ እንላለን..ሱፐርማርኬት ወጥቼ መሸማመት አለብኝ..መጠነኛ ድግስ ደግሳለው፣ማታ እንግዳ አለብኝ››
ንግግሯ ግራ አጋባውም.. ደነገጠም፡፡
‹‹የማታ እንግዳ ምን አይነት ነው?›› our
‹‹አንተም አለህበት…ዛሬ እዚህ ነው አይደል የምታድረው?››
እሷ ጋር እንዲያድር ስለጠየቀችው ደስ ብሏታል ..ግን እንግዳውስ…?ለመሆኑ ማን ነው
…?ሴት ነው ወንድ?፡፡‹‹እሺ ..እዚህ ነው የማድረው…ግን እንግዳውስ?››
‹‹እንግዲህ እሱን ከመጣ በኃላ ነው የምናውቀው…ልደር ካለ ግን እምቢ ማደር አትችልም የምለው አይነት ሰው አይደለም››በማለት ግራ አጋቢ መልስ ሰጠችው፡፡መልሷ ይብልጥ ቁርጠት ለቀቀበት…ይሄኔ ከመስሪያ ቤቷ ባለደረቦች አንዱ ነው….ሀለቃዋ ይሆን እንዴ…?ቢሆንስ ልደር ስላለ እንዴት እሺ ልትለው ትችላለች..?››ወይ ሴቶች ምን አይነት ቅኔ የሆኑ ፍጡሮች እንደሆኑ ሁሌ እንደደነቀው ነው፡፡ወንድም ሴትም በአንድ ላይ ሰው ተብሎ
መፈረጁ አግባብ አይደለም….አስተሳሰባችን እምነትና ፍላጎታችን ምኑም እኮ አይገናኝም››ሲል በውስጡ አብሰለሰለና..ነገሮች እስኪደርሱ ጠብቆ ለማየት ወሰነ…
‹‹ከዛ በፊ የተመቻቸ ጊዜ ካገኘው ነግራታለሁ…እንደውም ከማታው ፕሮግራሞ በፊት የእኔን ሀሳብ መስማት አለባት››የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ‹‹በቃ እንሂዳ››አላት፡፡
‹‹እሺ፣ተነስ ብላ ቦርሳዋን አንጠለጠለችና ተነሳች..ተያይዘው ወጡ ..ያለችው ሱፐር ማርኬት ይዛው ከገባች በኃላ ምትፈልገውን ነገሮች ሁሉ ተገዝተው በመኪናው ከተጫኑ በኃላ.. ማኪያቶ እንጠጣ ብሎ አንድ ፀጥተኛ ካፌ ይዞት ገባና..ፊት ለፊት እንደተቀመጡ እንደምንም እራሱን አጠንክሮ ወደነጥብ መንደርደር ጀመረ
‹‹ለምን ወደውጭ እንደሄድኩ ታውቂያለሽ አይደል?››
‹‹ሁለተኛ ዲግሪህን ለመማር ነዋ››
‹‹አይ ያማ ሽፋን ነው….እውነተኛ ምክንያቴን አንቺም በደንብ ታውቂዋለሽ..ወደውጭ የሄድኩት ባንቺ ተበሳጭቼ ነው፡፡››
‹‹አንተን ለማበሳጨት ብዬ ግን ምንም ያደረኩት ነገር የለም››
‹‹እሱን ማግባት አልነበረብሽም››
‹‹ለምን …ታዲያ አንተን ወንድሜን ማግባት ነበረብኝ?››
‹‹ምን ችግር አለው?እርግጥ እንደወንድምና እህት አንድቤት አድገናል..ግን የስጋ ትስስር አልነበረንም››
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አላዛር ቀኑን ሙሉ ሚስቱን ፍለጋ ሲባዝን ውሎ ሰባት ሰዓት አካባቢ ስልክ ተደወለለት..ቁጥሩን አያውቀውም…ግን ደግሞ ሰሎሜን ካገኛችሁ ደውሉልኝ ብሎ አደራ በማለት ስልኩን ለብዙ ሰው ስለሰጠ በትልቅ ተስፋና ጉጉት ነበር በፍጥነት ያነሳው፡፡
‹‹ሄሎ አላዛር ነህ?››ጎርናና ሻካራ የወንድ ድምፅ፡፡
‹‹አዎ ነኝ ፡፡ማን ልበል?››
‹‹ይሄንን ድምፅ አታውቀም?››
ተበሳጨ…ዛሬ የማንንም ሰው ድምፅ ለማወቅ ለአእምሮው የቤት ስራ የሚሰጥበት ሁኔታ ላይ አይደለም፡፡አንኳን የማያውቀውን ሰው ድምፅ የራሱንም ማንነት ለመርሳት ትንሽ ነው የቀረው‹‹ይቅርታ ማን ልበል..?እየነዳሁ ነው››አለ ኮስተር ብሎ፡፡
‹‹አሌክስ ነኝ››
በታላቅ ድንጋጤ መኪናውን ወደ ዳር አወጣና አቆማት…..
‹‹አሌክስ አልኬስ…አሌክሶ የእኛ እንዳትሆን?››
‹‹አዎ አሌክስ ነኝ…አሌክስ የእናንተው…የልጅነት እናም የጉርምስና ጊዜ ጓደኛችሁ››
‹‹ይገርማል…ፈፅሞ ያልጠበቅኩት ጉዳይ ነው…ለመሆኑ አለህ…?
ድሬደዋ እንዳለህ ሰምቼ ነበር..ግን ስልክህን ማግኘት ስላልቻልኩ ልደውልልህ አልቻልኩም፡፡››
‹‹አዎ አሁን ግን አዲስ አበባ ገብቼለሁ››
‹‹በጣም ይገርማል…አሌክሶ አሁን የሆነች ችግር ገጥሞኝ እሷን ለመፍታት እየተሯሯጥኩ ነው…..ይህ ያንተ ቁጥር ከሆነ ቆይቼ ልደውልልህ?››
‹‹ቆይ..እኔም ስለችግርህ ለማውራት ነው የደወልኩልህ››
አላዛር ድንግርግር አለው‹‹አልገባኝም?››
‹‹ችግርህ ስለሰሎሜ አይደለች..ማለቴ እሷን እየፈለክ አይደለህ?›››
የሚስቱን ስም ሲጠራ ይበልጥ ደነገጠ‹‹አዎ ግን እንዴት አወቅክ..ነው ወይስ እቴቴ ደውላልህ ነው?››
‹‹አይ…ከቴቴ ጋር አልተደዋወልንም.ሰሎሜ እኔ ጋር ነች››
አላዛር ይሄንን አረፍተ ነገር ሲሰማ ጭንቅላቱ ላይ ስል ሰይፍ አርፎ ለሁለት የሰነጠቀው ነው የመሰለው..በሰከንዶች ሽርፍራፊ ብዙ ብዙ ነገር ነው ያሰበው፡፡‹‹እንዴት እንዴት ብለው ተገናኙ?ከዚህ በፊትም በድብቅ ይገናኙ ነበር ማለት ነው…?እሱ እጅ ከገባች እንዴት ነው መልሼ የራሴ ላደርጋት የምችለው..?ነው ወይስ እስከወዲያኛው እያጣኋት ይሆን?፡፡››ሲል የስጋት ሀሳብ አሰበ፡፡
አለማየሁ ለረጅም ደቂቃዎች መልስ ሳይሰጠው ዝም ስላለበት ግራ ተጋብቶ ‹‹አላዛር…ምነው ዝም አልክ ..?ሰምተኸኛል?››
‹‹አዎ ሰምቼሀለው…ግን ምንም አልገባኝም…እንዴት ልታገኛት ቻልክ?››
‹‹እሱ ታሪኩ ረጅም ነው ..ናና እንነጋገራለን››
‹‹የት ነው የምመጣው?››
‹‹ፓሊስ ጣቢያ..ማለቴ…›› ብሎ ትክክለኛ አድራሻውን ነገረው፡፡
‹‹ፖሊስ ጣቢያ ምን ትሰራለች?››
‹‹አንተን ልትከስ መጥታ ልበልህ..?ለማንኛውም እየጠበቅኩህ ነው.. ፈጠን ብለህ ና››ብሎት ስልኩን ዘጋበት፡፡
አላዛር ድንዝዝ ነው ያለው…መኪናውና አንቀሳቅሶ በፍጥነት መሄድ እንዳለበት እንኳን ማስታወስ አላቻለም….‹‹የምን ክስ …?መቼስ ምንም አይን አውጣ ብትሆን ባሌ ከእኔ ጋር ግንኙነት አላደርግም አለኝ ›ብላ አትከሰኝም…..እንደዛማ አታደርግም…ደግሞ ካልጠፋ ቦታ ስንት ክፍለከተማ አቋርጣ እንዴት እዛ ድረስ …?እስከዛሬ እያወቀች እንዴት መቀየሩን ሳትነግረኝ ..?እንዲሁ እንደተብከነከነ እና የተንዛዙ ጥያቄዎች አእምሮውን አንዳጨናነቀ የተባለው ፓሊስ ጣቢያ ደረሰና መኪናውን ፓርክ አድርጎ ወደፖሊስ ጣቢያው ተጠጋ ፡፡በየት እንደሚገባ ግራ ተጋባ በራፍ እንዳለ ሆኖ በሆነ ሜትር ጠጋ ብሎ ደግሞ 5 ሜትር የሚሆን የተደርመሰ አጥር በግማሽ ቀልቡ እያየ ወደውስጥ ዘለቀና ለአለማየሁ ደወለለት፡፡
የቢሮውን ቁጥር ሲነግረው ፈራ ተባ እያለ አንኳኳና ወደውስጥ ገባ…ከስድስት አመት በፊት የተለየው የልጅነት ጓደኛውና አብሮ አደጉ ፊቱ በፂም ተሸፍኗ ትልቅ ሰው መስሎ እና የደንብ ልብሱን ለብሶ ተሸከርካሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ከእሱ ውጭ ክፉሉ ውስጥ ማንም የለም.ሰሎሜንም አገኛታለሁ ብሎ ጠብቆ ነበር…ግን እየታየችው አይደለም፡፡‹‹የት ወስዶ አስቀምጧት ነው?››በውስጡ አጉረመረመ፡፡
እንዴት ብሎ ሰላም እንደሚለው ግራ ገባው…‹‹ጓደኛዬን ለማግኘት ነው የመጣሁት ወይስ ተከስሼ ቃል ልሰጥ….?››ሲል እራሱን ጠየቀና ተደነጋሮት በራፍ ላይ ፈዞ ቆመ፡፡ አለማየሁ መቀመጫውን ለቆ መጣና ተጠመጠመበት…ከፍራቻው ጋር ሳይፋታ እሱም አቀፈውና የሞቀ ሳላምታ ተለዋወጡ ፡፡ይዞት ወደ ውስጥ ዘለቀና የሚቀመጥበት መቀመጫ ሰጠው..እሱም ከፊቱ ተቀመጠ….፡፡
አለማየሁ ደቂቃዎችን ወሰደና አላዛርን በትኩረት አየው፡፡አለባበሱ እንዳአንባሳደሮች ሽክ ያለ ነው..ደግሞ ልክ እንደድሮው …እንደውም ከዛም በላቀ ደረጃ ልቅም ያለቆንጆ ሆኗል፡፡ወንድን ልጅ ቆንጆ ነው ብሎ አያውቅም ፡፡ጓደኛውን የአላዛርን ቁንጅና ግን ፍጥጥ ያለ ስለሆነ ችላ ተብሎ የሚታለፍ አይነት አይደለም፡፡፡
ለንግግሩ አላዛር ቅድሚያውን ወሰደ‹‹በቅርብ ነው እዚህ የገባሀኸው?››
‹‹አዎ ገና ሁለት ወሬ ነው››
‹‹ሁለት ወር ሙሉ ስትቀመጥ እንዴት አስቻለህ? ነው ወይስ እኔ ብቻ ነኝ ያላገኘሁህ›?›
‹‹አይ ..እዚህ የተመደብኩት በሀላፊነት ቦታ ስለሆነ ነገሮችን እስክለማመዳቸውና እስኪዋሀዱኝ ወዲህ ወዲያ ማለት አልቻልኩም ነበር…መቼ እና እንዴት ላግኛቸው እያልኩ እያሰብኩ ሳለ ነው ድንገት ዛሬ ጥዋት ሰሎሜን ያገኘኋት፡፡››
‹‹ጥዋት?››
‹‹አዎ ጥዋት››
አላዛር ረጅም ትንፋሽ ወደ ውስጡ ሳበና እፎይ አለ…‹‹ለሊት ቀጥታ ከቤት እንደወጣች ወደእሱ ቤት ሄዳ ቢሆንስ ?››የሚል ጥርጣሬ ነበረው…እንደዛ ከሆነ ደግሞ ብዙ የሚፈጠሩና ወደኃላ ሊመለሱ የማይችሉ ችግሮች ይኖሩ እንደነበር ሲያሰላስል ስለቆየ ከአለማየሁ የሰማው መልስ በጣም ነው ያስደሰተው፡፡
‹‹ታዲያ አሁን የታለች?››
‹‹እስር ላይ ነች››
‹‹ምን?››የሚሰማውን አምኖ ለመቀበል ተቸገረ፡፡
የተሳሳተ ቃል የሰማ ነው የመሰለው….‹‹እሷ እስር ላይ !!እንዴት ተብሎ?››
‹‹ስትገባ ያየሀው መሰለኝ..አጥራችንን ለሊት የናደችው እሷ ነች››
‹‹ተረፈች ታዲያ ..?ተጎድታለች..?ሀኪም ቤት ወሰዳችሃት?››
‹‹አታስብ ..ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰባትም….››መኪናዋ ብቻ ትንሽ ተጫራለች…መንገድ ስለዘጋብን አንስተን ወደጎሮ አቁመናታል፡፡››
ከድንጋጤው ትንሽ ተንፈስ ብሎ‹‹መኪናዋ የራሷ ጉዳይ .እሷ ብቻ እንኳን ተረፈች››አለ ፡፡
‹‹አዎ..ተርፋለች››
ልመና ሳይሆን ትዕዛዝ በመሰለ ቃላት‹‹ላያት እፈልጋለሁ..››ሲል ተናገረ፡፡
‹‹ደህና ነች አልኩህ እኮ››
‹‹በፈጣሪ ካላየኋት አልረጋጋም…..በጓደኝነታችን..እባክህ?››
አለማየሁ ከዚህ በላይ ሊጨክንበት አልፈለገም፡፡‹‹አረ ችግር የለውም… እዚሁ አስመጣታለሁ…››አለና ከመቀመጫው ሳይነሳ ጠረጴዛው ላይ መጥሪያውን ተጫነው… ወዲያው አንድ ፖሊስ መጣና ወታደራዊ ሰላምታ ሰጥቶት የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ሆኖ ይጠብቅ ጀመረ
ኩማደር አለማሁም‹‹እስረኛ ሰሎሜ ግርማን ይዘህልኝ ና››ብሎ ትዕዛዙን አስተላለፈ፡፡
ፓሊሱ ወጥቶ ሄደ‹‹እስረኛ ሰሎሜ ግርማ ››ብሎ ሲናገር አላዛር ስቅጥጥ አለው፡፡
‹‹ኩማንደር ቆይ ግን አጥሩን እኔ በሁለት ቀን ውስጥ ሙሉውን ከበፊቱ በበለጠ አሳምሬ እስገናባዋለሁ….አስፈላጊም ከሆነም አሁኑኑ ደስ ያላችሁን ብር አስይዛለው..እሷ ማሰር እኮ አስፈላጊ አይደለም….››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አላዛር ቀኑን ሙሉ ሚስቱን ፍለጋ ሲባዝን ውሎ ሰባት ሰዓት አካባቢ ስልክ ተደወለለት..ቁጥሩን አያውቀውም…ግን ደግሞ ሰሎሜን ካገኛችሁ ደውሉልኝ ብሎ አደራ በማለት ስልኩን ለብዙ ሰው ስለሰጠ በትልቅ ተስፋና ጉጉት ነበር በፍጥነት ያነሳው፡፡
‹‹ሄሎ አላዛር ነህ?››ጎርናና ሻካራ የወንድ ድምፅ፡፡
‹‹አዎ ነኝ ፡፡ማን ልበል?››
‹‹ይሄንን ድምፅ አታውቀም?››
ተበሳጨ…ዛሬ የማንንም ሰው ድምፅ ለማወቅ ለአእምሮው የቤት ስራ የሚሰጥበት ሁኔታ ላይ አይደለም፡፡አንኳን የማያውቀውን ሰው ድምፅ የራሱንም ማንነት ለመርሳት ትንሽ ነው የቀረው‹‹ይቅርታ ማን ልበል..?እየነዳሁ ነው››አለ ኮስተር ብሎ፡፡
‹‹አሌክስ ነኝ››
በታላቅ ድንጋጤ መኪናውን ወደ ዳር አወጣና አቆማት…..
‹‹አሌክስ አልኬስ…አሌክሶ የእኛ እንዳትሆን?››
‹‹አዎ አሌክስ ነኝ…አሌክስ የእናንተው…የልጅነት እናም የጉርምስና ጊዜ ጓደኛችሁ››
‹‹ይገርማል…ፈፅሞ ያልጠበቅኩት ጉዳይ ነው…ለመሆኑ አለህ…?
ድሬደዋ እንዳለህ ሰምቼ ነበር..ግን ስልክህን ማግኘት ስላልቻልኩ ልደውልልህ አልቻልኩም፡፡››
‹‹አዎ አሁን ግን አዲስ አበባ ገብቼለሁ››
‹‹በጣም ይገርማል…አሌክሶ አሁን የሆነች ችግር ገጥሞኝ እሷን ለመፍታት እየተሯሯጥኩ ነው…..ይህ ያንተ ቁጥር ከሆነ ቆይቼ ልደውልልህ?››
‹‹ቆይ..እኔም ስለችግርህ ለማውራት ነው የደወልኩልህ››
አላዛር ድንግርግር አለው‹‹አልገባኝም?››
‹‹ችግርህ ስለሰሎሜ አይደለች..ማለቴ እሷን እየፈለክ አይደለህ?›››
የሚስቱን ስም ሲጠራ ይበልጥ ደነገጠ‹‹አዎ ግን እንዴት አወቅክ..ነው ወይስ እቴቴ ደውላልህ ነው?››
‹‹አይ…ከቴቴ ጋር አልተደዋወልንም.ሰሎሜ እኔ ጋር ነች››
አላዛር ይሄንን አረፍተ ነገር ሲሰማ ጭንቅላቱ ላይ ስል ሰይፍ አርፎ ለሁለት የሰነጠቀው ነው የመሰለው..በሰከንዶች ሽርፍራፊ ብዙ ብዙ ነገር ነው ያሰበው፡፡‹‹እንዴት እንዴት ብለው ተገናኙ?ከዚህ በፊትም በድብቅ ይገናኙ ነበር ማለት ነው…?እሱ እጅ ከገባች እንዴት ነው መልሼ የራሴ ላደርጋት የምችለው..?ነው ወይስ እስከወዲያኛው እያጣኋት ይሆን?፡፡››ሲል የስጋት ሀሳብ አሰበ፡፡
አለማየሁ ለረጅም ደቂቃዎች መልስ ሳይሰጠው ዝም ስላለበት ግራ ተጋብቶ ‹‹አላዛር…ምነው ዝም አልክ ..?ሰምተኸኛል?››
‹‹አዎ ሰምቼሀለው…ግን ምንም አልገባኝም…እንዴት ልታገኛት ቻልክ?››
‹‹እሱ ታሪኩ ረጅም ነው ..ናና እንነጋገራለን››
‹‹የት ነው የምመጣው?››
‹‹ፓሊስ ጣቢያ..ማለቴ…›› ብሎ ትክክለኛ አድራሻውን ነገረው፡፡
‹‹ፖሊስ ጣቢያ ምን ትሰራለች?››
‹‹አንተን ልትከስ መጥታ ልበልህ..?ለማንኛውም እየጠበቅኩህ ነው.. ፈጠን ብለህ ና››ብሎት ስልኩን ዘጋበት፡፡
አላዛር ድንዝዝ ነው ያለው…መኪናውና አንቀሳቅሶ በፍጥነት መሄድ እንዳለበት እንኳን ማስታወስ አላቻለም….‹‹የምን ክስ …?መቼስ ምንም አይን አውጣ ብትሆን ባሌ ከእኔ ጋር ግንኙነት አላደርግም አለኝ ›ብላ አትከሰኝም…..እንደዛማ አታደርግም…ደግሞ ካልጠፋ ቦታ ስንት ክፍለከተማ አቋርጣ እንዴት እዛ ድረስ …?እስከዛሬ እያወቀች እንዴት መቀየሩን ሳትነግረኝ ..?እንዲሁ እንደተብከነከነ እና የተንዛዙ ጥያቄዎች አእምሮውን አንዳጨናነቀ የተባለው ፓሊስ ጣቢያ ደረሰና መኪናውን ፓርክ አድርጎ ወደፖሊስ ጣቢያው ተጠጋ ፡፡በየት እንደሚገባ ግራ ተጋባ በራፍ እንዳለ ሆኖ በሆነ ሜትር ጠጋ ብሎ ደግሞ 5 ሜትር የሚሆን የተደርመሰ አጥር በግማሽ ቀልቡ እያየ ወደውስጥ ዘለቀና ለአለማየሁ ደወለለት፡፡
የቢሮውን ቁጥር ሲነግረው ፈራ ተባ እያለ አንኳኳና ወደውስጥ ገባ…ከስድስት አመት በፊት የተለየው የልጅነት ጓደኛውና አብሮ አደጉ ፊቱ በፂም ተሸፍኗ ትልቅ ሰው መስሎ እና የደንብ ልብሱን ለብሶ ተሸከርካሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ከእሱ ውጭ ክፉሉ ውስጥ ማንም የለም.ሰሎሜንም አገኛታለሁ ብሎ ጠብቆ ነበር…ግን እየታየችው አይደለም፡፡‹‹የት ወስዶ አስቀምጧት ነው?››በውስጡ አጉረመረመ፡፡
እንዴት ብሎ ሰላም እንደሚለው ግራ ገባው…‹‹ጓደኛዬን ለማግኘት ነው የመጣሁት ወይስ ተከስሼ ቃል ልሰጥ….?››ሲል እራሱን ጠየቀና ተደነጋሮት በራፍ ላይ ፈዞ ቆመ፡፡ አለማየሁ መቀመጫውን ለቆ መጣና ተጠመጠመበት…ከፍራቻው ጋር ሳይፋታ እሱም አቀፈውና የሞቀ ሳላምታ ተለዋወጡ ፡፡ይዞት ወደ ውስጥ ዘለቀና የሚቀመጥበት መቀመጫ ሰጠው..እሱም ከፊቱ ተቀመጠ….፡፡
አለማየሁ ደቂቃዎችን ወሰደና አላዛርን በትኩረት አየው፡፡አለባበሱ እንዳአንባሳደሮች ሽክ ያለ ነው..ደግሞ ልክ እንደድሮው …እንደውም ከዛም በላቀ ደረጃ ልቅም ያለቆንጆ ሆኗል፡፡ወንድን ልጅ ቆንጆ ነው ብሎ አያውቅም ፡፡ጓደኛውን የአላዛርን ቁንጅና ግን ፍጥጥ ያለ ስለሆነ ችላ ተብሎ የሚታለፍ አይነት አይደለም፡፡፡
ለንግግሩ አላዛር ቅድሚያውን ወሰደ‹‹በቅርብ ነው እዚህ የገባሀኸው?››
‹‹አዎ ገና ሁለት ወሬ ነው››
‹‹ሁለት ወር ሙሉ ስትቀመጥ እንዴት አስቻለህ? ነው ወይስ እኔ ብቻ ነኝ ያላገኘሁህ›?›
‹‹አይ ..እዚህ የተመደብኩት በሀላፊነት ቦታ ስለሆነ ነገሮችን እስክለማመዳቸውና እስኪዋሀዱኝ ወዲህ ወዲያ ማለት አልቻልኩም ነበር…መቼ እና እንዴት ላግኛቸው እያልኩ እያሰብኩ ሳለ ነው ድንገት ዛሬ ጥዋት ሰሎሜን ያገኘኋት፡፡››
‹‹ጥዋት?››
‹‹አዎ ጥዋት››
አላዛር ረጅም ትንፋሽ ወደ ውስጡ ሳበና እፎይ አለ…‹‹ለሊት ቀጥታ ከቤት እንደወጣች ወደእሱ ቤት ሄዳ ቢሆንስ ?››የሚል ጥርጣሬ ነበረው…እንደዛ ከሆነ ደግሞ ብዙ የሚፈጠሩና ወደኃላ ሊመለሱ የማይችሉ ችግሮች ይኖሩ እንደነበር ሲያሰላስል ስለቆየ ከአለማየሁ የሰማው መልስ በጣም ነው ያስደሰተው፡፡
‹‹ታዲያ አሁን የታለች?››
‹‹እስር ላይ ነች››
‹‹ምን?››የሚሰማውን አምኖ ለመቀበል ተቸገረ፡፡
የተሳሳተ ቃል የሰማ ነው የመሰለው….‹‹እሷ እስር ላይ !!እንዴት ተብሎ?››
‹‹ስትገባ ያየሀው መሰለኝ..አጥራችንን ለሊት የናደችው እሷ ነች››
‹‹ተረፈች ታዲያ ..?ተጎድታለች..?ሀኪም ቤት ወሰዳችሃት?››
‹‹አታስብ ..ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰባትም….››መኪናዋ ብቻ ትንሽ ተጫራለች…መንገድ ስለዘጋብን አንስተን ወደጎሮ አቁመናታል፡፡››
ከድንጋጤው ትንሽ ተንፈስ ብሎ‹‹መኪናዋ የራሷ ጉዳይ .እሷ ብቻ እንኳን ተረፈች››አለ ፡፡
‹‹አዎ..ተርፋለች››
ልመና ሳይሆን ትዕዛዝ በመሰለ ቃላት‹‹ላያት እፈልጋለሁ..››ሲል ተናገረ፡፡
‹‹ደህና ነች አልኩህ እኮ››
‹‹በፈጣሪ ካላየኋት አልረጋጋም…..በጓደኝነታችን..እባክህ?››
አለማየሁ ከዚህ በላይ ሊጨክንበት አልፈለገም፡፡‹‹አረ ችግር የለውም… እዚሁ አስመጣታለሁ…››አለና ከመቀመጫው ሳይነሳ ጠረጴዛው ላይ መጥሪያውን ተጫነው… ወዲያው አንድ ፖሊስ መጣና ወታደራዊ ሰላምታ ሰጥቶት የሚለውን ለመስማት ዝግጁ ሆኖ ይጠብቅ ጀመረ
ኩማደር አለማሁም‹‹እስረኛ ሰሎሜ ግርማን ይዘህልኝ ና››ብሎ ትዕዛዙን አስተላለፈ፡፡
ፓሊሱ ወጥቶ ሄደ‹‹እስረኛ ሰሎሜ ግርማ ››ብሎ ሲናገር አላዛር ስቅጥጥ አለው፡፡
‹‹ኩማንደር ቆይ ግን አጥሩን እኔ በሁለት ቀን ውስጥ ሙሉውን ከበፊቱ በበለጠ አሳምሬ እስገናባዋለሁ….አስፈላጊም ከሆነም አሁኑኑ ደስ ያላችሁን ብር አስይዛለው..እሷ ማሰር እኮ አስፈላጊ አይደለም….››