#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...እሷም አያቷም ታጥበው እንደተመለሱ፣ ራት በልተው በየክፍላቸው ገብተው ተኙ።
ወለተጊዮርጊስ፣ ጠዋት ከእንቅልፏ ስትነቃ የት እንዳለች ግራ ገባት።ቀስ በቀስ ጐንደር ቤተመንግሥት፣ እንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ መሆኗ ተገለጠላት። በመስኮቱ ቀዳዳዎች የገባውን ብርሃን አይታ ፀሐይ መውጣቷን አወቀች። አርፍዳ እንደነቃች ገባት፡፡ ምን ማድረግ እንዳለባት ግራ ገብቷት እዛው አረፍ ብላ ቆየች። ሲሰለቻት ተነስታ ስትወጣ፣ በር ላይ ቆመው የእሷን መውጣት የሚጠባበቁ ሁለት
ደንገጡሮች አያቷ ወዳሉበት ክፍል ወሰዷት።
አያቷ መስኮቱን ከፍተው አልጋው ላይ ጋደም ብለው የጸሎት
መጽሐፍ ያነባሉ። ስትገባ መጽሐፉን አስቀምጠው፣ “አድረሽ ነው? ሲሏት ደሕና ማደሯን ለመግለጽ እግራቸው ላይ ተጠመጠመች።በይ ተነሽ አሏት፣ ስሜታቸው ተነክቶ። ትንሽ እንደቆዩ ደንገጡሮቹ መጡላቸው። መፀዳጃ ቤት ወስደዋቸው ሲመለሱ ቁርስ አደረጉ።
ዮልያና ያረፉበት ክፍል ተመልሰው ስለ ምሳው ተወያዩ።
“ዛሬ እንግዲህ ኸጃንሆይ ጋር ማድ ምቀርቢበት ቀን ነው። እናም የነገርሁሽን ሁሉ ልብ እንድትይ። እንደገባሽ ኸደሽ በቅጡ አጎንብሰሽ እጅ ትነሽና እግር ትስሚያለሽ። ተቀመጭ እስቲለሽ ትጠብቂና ያመላከቱሽ ቦታ ኸደሽ ትቀመጫለሽ...”
የጀመሩትን ሳይጨርሱ ሁለት ደንገጡሮች በር ላይ ሆነው ለጥ ብለው እጅ ከነሱ በኋላ፣ አንደኛዋ፣ “እመቤቶቼ እንፋሎት እጥበት
እንኸዳ” አለቻቸው።
ወለተጊዮርጊስና አያቷ በደንገጡሮቹ ተከታይነት የአፄ ፋሲልንና የታላቁ ኢያሱን ቤተመንግሥታት ከኋላቸው ትተው ወደ ታች ወረዱ። የጻድቁ ዮሐንስን ቤተመዛግብት በግራ በኩል፣ ቤተመንግሥታቸውን
ወለተጊዮርጊስ በወሬ እንጂ በአካል አይታቸው የማታውቃቸውንና በስተቀኝ አልፈው፣ አንበሶቹ ቤትጋ ሲደርሱ አያቷ፣ “አንበሶች” ሲሉ ጠዋት ላይ ሲያገሱ የሰማቻቸውን አንበሶች ለማየት ቆም አለች። በአድናቆት ካስተዋለቻቸው በኋላ፣ከአንበሶቹ ቤት ጀርባ ያለውን የሣልሳዊ ዳዊትን የሙዚቃ አዳራሽ አሁንም በቀኝ በኩል ትተው ወደ ፊት አመሩ። ወለተጊዮርጊስ በየቤተመንግሥታቱ መተላለፊያ ላይ የተሰደሩት ወታደሮችና በየበሩ ላይ የቆሙት እልፍኝ አስከልካዮች
ቁጥር አስገረማት፣ ከእነሱ ጋር የመፋጠጥ ያህል ተሰማት። በመጨረሻም ቁመቱ አጠር ያለ ነገር ግን ሰፋ ያለ ግንብ ውስጥ ገቡ።
“እመቤቶቼ እኼ ንጉሦቹና እቴጌዎቹ እንፋሎት ሚገቡበት ነው” አለቻቸው፣ ከደንገጡሮቹ አንዷ ። ቀጥላም፣ “አጤ ፋሲል ናቸው ያሠሩት። እኼኛው የእቴጌዎቹ ነው። የንጉሦቹ በያኛው በኩል ነው።ልብሳችሁን ታወልቁና እነዝኸ መንጠቆዎች ላይ ትሰቅላላችሁ።ጌጦቻችሁን ደሞ እነዝኸ ውስጥ ታኖራላችሁ” አለቻቸው፣ ትንንሾቹን የድንጋይ ፉካዎች በሌባ ጣቷ እያመለከተቻቸው።
“በዝኸ በር ግቡና ኸነዛ ዳርና ዳር ያሉ መቀመጫዎች ላይ ተቀመጡ። ያ ሚጨሰው አረግ እሬሳና ጦስኝ ነው። እኛ ከውጭ ሁነን እንጠብቃለን” ብላቸው ከሌላዋ ደንገጡር ጋር ተያይዘው ወጡ።
ወለተጊዮርጊስና ዮልያና ጌጦቻቸውን አስቀምጠው፣ ልብሳቸውን አውልቀው የተባለው ክፍል ውስጥ አጎንብሰው ገብተው ተቀመጡ።ክፍሉ መሃል ላይ የተደረደሩት ድንጋዮች ሲግሉ፣ “አየሽ ያነን ምታይውን ወናፍ በዚያች በምታያት ቀዳዳ አሳልፈው፣ ኸውጭ ሁነው
ደንጊያዎቹን ያግላሉ” አሏት።
ድንጋዮቹ ሲግሉ፣ ከውጭ በቀርከሀ ዋሽንት ውሃ ድንጋዮቹ ላይ ፈሰሰ። ላብ አጠመቃቸው። እንደመታፈን ሲሉ ከጣሪያው ላይ ያሉት ትንንሽ ቀዳዳዎች ከውጭ ተከፈቱላቸው።
“አየር እንዲገባ ቀዳዳዎቹን ከፈቱልን። አለያማ ታፍነን እንሞት
ነበር” አሏት።
ቀዳዳዎቹ ተመልሰው ተዘጉ።
“እንፋሎት ተመልሶ እንዲመጣልን መልሰው ዘጉት” አለች፣ ነገሩ
የገባት ወለተጊዮርጊስ።
“እንዲህ አይሁን እንጂ እኛም እኮ በእንፋሎት መታጠብ እናውቃለን
አሉ፣ ዮልያና።
እሷ ይህን ዓይነቱን ነገር ከእሳቸው ቀርቶ ከማንም ጋር አድርጋው
ባለማወቋ እፍረቱ አላስቀምጥ አላት። ሰውነቷ እየተሟሟቀ ሲመጣ ግን ዘና አለች። ከፊቷና ከራሷ ላይ የሚፈልቀውን ላብ አስር ጊዜ ስትጠራርግ አዩና፣ “አይዞሽ አሁን ያነን ሁሉ የምንገድ ድካም ድራሹን ነው ሚያጠፋልሽ” አሏት።
ሲጨርሱ ወደ ገላ መታጠቢያው ክፍል ሄደው ዙርያውን የተከበበ
ገንዳ ውስጥ መጀመሪያ እሳቸው፣ ቀጥሎ እሷ ታጥበው የክት ልብሳቸውን ለብሰው ሲወጡ፣ ወለተጊዮርጊስ ከመቼውም ጊዜ በላይ አለምልማለች።
ዕረፍት እንዲያደርጉ ማረፊያ ክፍሎቻቸው ተወሰዱ።
ብዙም ሳይቆዩ ደንገጡሮቹ ለወለተጊዮርጊስ በእቅፋቸው ነጭ ረጅም የሐር ቀሚስ፣ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች ያጌጠ ጥቁር ካባ፣ የቆዳ ጫማ፣ ነጭ የሐር ሻሽና ከወርቅ የተሠሩ የአንገትና የጆሮ ጌጦች ይዘው መጡ። አንደኛዋ ታጥቦ የነበረውን ፀጉሯን ሾርባላት ሄዱ።ወለተጊዮርጊስ የመጣላትን ልብስ፣ ካባ፣ ሻሽ፣ ጫማና ጌጦች ግልጽ በሆነ አድናቆት አገላብጣ ስታይ፣ ጋደም ብለው የነበሩት አያቷ አይዋት።
በለጋ ዕድሜዋ እዚህ ደረጃ በመድረሷ ተደስተው እንባቸው ቀረር አለ። እንባቸው እንዳታይባቸው በነጠላቸው ተሸፍነው ፊታቸውን ወደ
ግድግዳው አዞሩ። ራሳቸውን አረጋግተው ነጠላቸውን ከፊታቸው ላይ ገለጥ አደረጉና ወደ እሷ ዞሩ። አሁንም የመጣላትን ዕቃ ታገላብጣለች።
“ጥሎሽ የመጣልሽም ኸዝኸ ይበልጥ እንጂ አይተናነስም። እሱን ልበሺ ስልሽ ለመንገድ አይሆንም ብለሽ የኔን ለበሽ። ለማንኛውም ጥሎሽ ይለቅ። አሁን እሱን አስቀምጭና ወደ ጃንሆይ ስትኸጂ እንዴት እንደሆነ አንዴ ተወጪልኝ” አሏት።
ልብሶቹን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አኑራ፣ ክብ ዐይኖቿን ሰበር አድርጋ
በተመጠነ፣ ንግሥታዊ በሚመስል እርምጃ ወደ እሳቸው ስትጠጋ፣ “እኼ ነው የኔ ልዥ ። ያሳየሁሽን ሁሉ አረሳሽም። እንዲያውም አክለሽበታል” አሉና ጠጋ እንድትላቸው በእጃቸው ጠቆሟት። ተጠግታቸው
ስታጎነብስ፣ “እንዲህ ያለች ምሽት ኸየትም አያገኙ” ብለው ጉንጫን
መታ አደረጓት።
ቀና አለችና የእፍረት ሳቅ ሳቀች። “ስንት መልከ መልካም ወይዛዝርት
አለ በሚባልበት... ስንት የንጉሥ ዘር ባለበት አገር?” አለቻቸው።
በስጨት እንደማለት ብለው፣ “አንቺ ደሞ እንግዲህ ሰው ሚልሽን ስሚ አሉና ከተጋደሙበት ተነሥተው ተቀመጡ። ወገባቸውን በሁለት እጃቸው ይዘው፣ “የንጉሥ ዘር የሆነ ሁሉ መልክ አለው መሰለሽ? አንቺ ሁሉን አሟልቶ ሰቶሻል። ደሞ ጃንሆይ የንጉሥ ዘር ቢፈልጉ አጥተው? አንቺስ ብትሆኚ የንጉሥ ዘር ማዶለሽ? አንድ መኰንን አልገዛም ብሎ
ሲያውክ በጋብቻ ለማሰር፣ ጥቅም ለማስጠበቅ አሊያም ደሞ አመጥ
ለማብረድ ሲሉ መሰለሽ አንቺን ማግባት የፈለጉ? ወደውሽ ነው።
ትምርትም ቢሆን ዳዊት ደግመሻል። ጥፈትም ቢሆን ሚደርስብሽ የለ። የጐንደር ወይዛዝርት እኩሌታዎቹ ስንኳ ዳዊት አልደገሙም...
ይቅር ኻንቺ ሊተካከሉ... ኧረ እንዲያው ምንሽም አይደርሱ።”
“አየ እሚታዬ ልዥሽ ስለ ሆንኩ ነው እንደሱ ምትይው። ግና ኣንድ
ጥያቄ ልጠይቅሽ... ጃንሆይ ኸዝኸ በፊት አላገቡም ነበር እንዴ?”
“አግብተው ነበር እንጂ።”
“እህስ?”
“በእንዴት ያለ ወግ ተጋብተው እሷ የሠርጉ ምሽት እንደ ወጉ ግብር
አብልታ፣ እህል ውሃ ስንኳ ሳትቀምስ በጥኑ ታማ በበነጋው ሞተች።እደብረብርሃን ሥላሤ ነው የተቀበረች፤ ኸዛው እናታቸው ኻሉበት። መርዝ ነው ይላሉ። እንዴት ያለች አለላና ብርቱ ሴት ነበረች አሉ። ደማምና ብርቱ ይሆናቸዋል።”
“እንዴ?” አለች ወለተጊዮርጊስ፣ ሰውነቷን ያልታወቀ ነገር ወረር
አድርጓት። ተነስታ ቆመች። “እኔስ ፈራሁ። እኔንስ በመርዝ ቢገሉኝ?"
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...እሷም አያቷም ታጥበው እንደተመለሱ፣ ራት በልተው በየክፍላቸው ገብተው ተኙ።
ወለተጊዮርጊስ፣ ጠዋት ከእንቅልፏ ስትነቃ የት እንዳለች ግራ ገባት።ቀስ በቀስ ጐንደር ቤተመንግሥት፣ እንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ መሆኗ ተገለጠላት። በመስኮቱ ቀዳዳዎች የገባውን ብርሃን አይታ ፀሐይ መውጣቷን አወቀች። አርፍዳ እንደነቃች ገባት፡፡ ምን ማድረግ እንዳለባት ግራ ገብቷት እዛው አረፍ ብላ ቆየች። ሲሰለቻት ተነስታ ስትወጣ፣ በር ላይ ቆመው የእሷን መውጣት የሚጠባበቁ ሁለት
ደንገጡሮች አያቷ ወዳሉበት ክፍል ወሰዷት።
አያቷ መስኮቱን ከፍተው አልጋው ላይ ጋደም ብለው የጸሎት
መጽሐፍ ያነባሉ። ስትገባ መጽሐፉን አስቀምጠው፣ “አድረሽ ነው? ሲሏት ደሕና ማደሯን ለመግለጽ እግራቸው ላይ ተጠመጠመች።በይ ተነሽ አሏት፣ ስሜታቸው ተነክቶ። ትንሽ እንደቆዩ ደንገጡሮቹ መጡላቸው። መፀዳጃ ቤት ወስደዋቸው ሲመለሱ ቁርስ አደረጉ።
ዮልያና ያረፉበት ክፍል ተመልሰው ስለ ምሳው ተወያዩ።
“ዛሬ እንግዲህ ኸጃንሆይ ጋር ማድ ምቀርቢበት ቀን ነው። እናም የነገርሁሽን ሁሉ ልብ እንድትይ። እንደገባሽ ኸደሽ በቅጡ አጎንብሰሽ እጅ ትነሽና እግር ትስሚያለሽ። ተቀመጭ እስቲለሽ ትጠብቂና ያመላከቱሽ ቦታ ኸደሽ ትቀመጫለሽ...”
የጀመሩትን ሳይጨርሱ ሁለት ደንገጡሮች በር ላይ ሆነው ለጥ ብለው እጅ ከነሱ በኋላ፣ አንደኛዋ፣ “እመቤቶቼ እንፋሎት እጥበት
እንኸዳ” አለቻቸው።
ወለተጊዮርጊስና አያቷ በደንገጡሮቹ ተከታይነት የአፄ ፋሲልንና የታላቁ ኢያሱን ቤተመንግሥታት ከኋላቸው ትተው ወደ ታች ወረዱ። የጻድቁ ዮሐንስን ቤተመዛግብት በግራ በኩል፣ ቤተመንግሥታቸውን
ወለተጊዮርጊስ በወሬ እንጂ በአካል አይታቸው የማታውቃቸውንና በስተቀኝ አልፈው፣ አንበሶቹ ቤትጋ ሲደርሱ አያቷ፣ “አንበሶች” ሲሉ ጠዋት ላይ ሲያገሱ የሰማቻቸውን አንበሶች ለማየት ቆም አለች። በአድናቆት ካስተዋለቻቸው በኋላ፣ከአንበሶቹ ቤት ጀርባ ያለውን የሣልሳዊ ዳዊትን የሙዚቃ አዳራሽ አሁንም በቀኝ በኩል ትተው ወደ ፊት አመሩ። ወለተጊዮርጊስ በየቤተመንግሥታቱ መተላለፊያ ላይ የተሰደሩት ወታደሮችና በየበሩ ላይ የቆሙት እልፍኝ አስከልካዮች
ቁጥር አስገረማት፣ ከእነሱ ጋር የመፋጠጥ ያህል ተሰማት። በመጨረሻም ቁመቱ አጠር ያለ ነገር ግን ሰፋ ያለ ግንብ ውስጥ ገቡ።
“እመቤቶቼ እኼ ንጉሦቹና እቴጌዎቹ እንፋሎት ሚገቡበት ነው” አለቻቸው፣ ከደንገጡሮቹ አንዷ ። ቀጥላም፣ “አጤ ፋሲል ናቸው ያሠሩት። እኼኛው የእቴጌዎቹ ነው። የንጉሦቹ በያኛው በኩል ነው።ልብሳችሁን ታወልቁና እነዝኸ መንጠቆዎች ላይ ትሰቅላላችሁ።ጌጦቻችሁን ደሞ እነዝኸ ውስጥ ታኖራላችሁ” አለቻቸው፣ ትንንሾቹን የድንጋይ ፉካዎች በሌባ ጣቷ እያመለከተቻቸው።
“በዝኸ በር ግቡና ኸነዛ ዳርና ዳር ያሉ መቀመጫዎች ላይ ተቀመጡ። ያ ሚጨሰው አረግ እሬሳና ጦስኝ ነው። እኛ ከውጭ ሁነን እንጠብቃለን” ብላቸው ከሌላዋ ደንገጡር ጋር ተያይዘው ወጡ።
ወለተጊዮርጊስና ዮልያና ጌጦቻቸውን አስቀምጠው፣ ልብሳቸውን አውልቀው የተባለው ክፍል ውስጥ አጎንብሰው ገብተው ተቀመጡ።ክፍሉ መሃል ላይ የተደረደሩት ድንጋዮች ሲግሉ፣ “አየሽ ያነን ምታይውን ወናፍ በዚያች በምታያት ቀዳዳ አሳልፈው፣ ኸውጭ ሁነው
ደንጊያዎቹን ያግላሉ” አሏት።
ድንጋዮቹ ሲግሉ፣ ከውጭ በቀርከሀ ዋሽንት ውሃ ድንጋዮቹ ላይ ፈሰሰ። ላብ አጠመቃቸው። እንደመታፈን ሲሉ ከጣሪያው ላይ ያሉት ትንንሽ ቀዳዳዎች ከውጭ ተከፈቱላቸው።
“አየር እንዲገባ ቀዳዳዎቹን ከፈቱልን። አለያማ ታፍነን እንሞት
ነበር” አሏት።
ቀዳዳዎቹ ተመልሰው ተዘጉ።
“እንፋሎት ተመልሶ እንዲመጣልን መልሰው ዘጉት” አለች፣ ነገሩ
የገባት ወለተጊዮርጊስ።
“እንዲህ አይሁን እንጂ እኛም እኮ በእንፋሎት መታጠብ እናውቃለን
አሉ፣ ዮልያና።
እሷ ይህን ዓይነቱን ነገር ከእሳቸው ቀርቶ ከማንም ጋር አድርጋው
ባለማወቋ እፍረቱ አላስቀምጥ አላት። ሰውነቷ እየተሟሟቀ ሲመጣ ግን ዘና አለች። ከፊቷና ከራሷ ላይ የሚፈልቀውን ላብ አስር ጊዜ ስትጠራርግ አዩና፣ “አይዞሽ አሁን ያነን ሁሉ የምንገድ ድካም ድራሹን ነው ሚያጠፋልሽ” አሏት።
ሲጨርሱ ወደ ገላ መታጠቢያው ክፍል ሄደው ዙርያውን የተከበበ
ገንዳ ውስጥ መጀመሪያ እሳቸው፣ ቀጥሎ እሷ ታጥበው የክት ልብሳቸውን ለብሰው ሲወጡ፣ ወለተጊዮርጊስ ከመቼውም ጊዜ በላይ አለምልማለች።
ዕረፍት እንዲያደርጉ ማረፊያ ክፍሎቻቸው ተወሰዱ።
ብዙም ሳይቆዩ ደንገጡሮቹ ለወለተጊዮርጊስ በእቅፋቸው ነጭ ረጅም የሐር ቀሚስ፣ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች ያጌጠ ጥቁር ካባ፣ የቆዳ ጫማ፣ ነጭ የሐር ሻሽና ከወርቅ የተሠሩ የአንገትና የጆሮ ጌጦች ይዘው መጡ። አንደኛዋ ታጥቦ የነበረውን ፀጉሯን ሾርባላት ሄዱ።ወለተጊዮርጊስ የመጣላትን ልብስ፣ ካባ፣ ሻሽ፣ ጫማና ጌጦች ግልጽ በሆነ አድናቆት አገላብጣ ስታይ፣ ጋደም ብለው የነበሩት አያቷ አይዋት።
በለጋ ዕድሜዋ እዚህ ደረጃ በመድረሷ ተደስተው እንባቸው ቀረር አለ። እንባቸው እንዳታይባቸው በነጠላቸው ተሸፍነው ፊታቸውን ወደ
ግድግዳው አዞሩ። ራሳቸውን አረጋግተው ነጠላቸውን ከፊታቸው ላይ ገለጥ አደረጉና ወደ እሷ ዞሩ። አሁንም የመጣላትን ዕቃ ታገላብጣለች።
“ጥሎሽ የመጣልሽም ኸዝኸ ይበልጥ እንጂ አይተናነስም። እሱን ልበሺ ስልሽ ለመንገድ አይሆንም ብለሽ የኔን ለበሽ። ለማንኛውም ጥሎሽ ይለቅ። አሁን እሱን አስቀምጭና ወደ ጃንሆይ ስትኸጂ እንዴት እንደሆነ አንዴ ተወጪልኝ” አሏት።
ልብሶቹን አልጋው ላይ በጥንቃቄ አኑራ፣ ክብ ዐይኖቿን ሰበር አድርጋ
በተመጠነ፣ ንግሥታዊ በሚመስል እርምጃ ወደ እሳቸው ስትጠጋ፣ “እኼ ነው የኔ ልዥ ። ያሳየሁሽን ሁሉ አረሳሽም። እንዲያውም አክለሽበታል” አሉና ጠጋ እንድትላቸው በእጃቸው ጠቆሟት። ተጠግታቸው
ስታጎነብስ፣ “እንዲህ ያለች ምሽት ኸየትም አያገኙ” ብለው ጉንጫን
መታ አደረጓት።
ቀና አለችና የእፍረት ሳቅ ሳቀች። “ስንት መልከ መልካም ወይዛዝርት
አለ በሚባልበት... ስንት የንጉሥ ዘር ባለበት አገር?” አለቻቸው።
በስጨት እንደማለት ብለው፣ “አንቺ ደሞ እንግዲህ ሰው ሚልሽን ስሚ አሉና ከተጋደሙበት ተነሥተው ተቀመጡ። ወገባቸውን በሁለት እጃቸው ይዘው፣ “የንጉሥ ዘር የሆነ ሁሉ መልክ አለው መሰለሽ? አንቺ ሁሉን አሟልቶ ሰቶሻል። ደሞ ጃንሆይ የንጉሥ ዘር ቢፈልጉ አጥተው? አንቺስ ብትሆኚ የንጉሥ ዘር ማዶለሽ? አንድ መኰንን አልገዛም ብሎ
ሲያውክ በጋብቻ ለማሰር፣ ጥቅም ለማስጠበቅ አሊያም ደሞ አመጥ
ለማብረድ ሲሉ መሰለሽ አንቺን ማግባት የፈለጉ? ወደውሽ ነው።
ትምርትም ቢሆን ዳዊት ደግመሻል። ጥፈትም ቢሆን ሚደርስብሽ የለ። የጐንደር ወይዛዝርት እኩሌታዎቹ ስንኳ ዳዊት አልደገሙም...
ይቅር ኻንቺ ሊተካከሉ... ኧረ እንዲያው ምንሽም አይደርሱ።”
“አየ እሚታዬ ልዥሽ ስለ ሆንኩ ነው እንደሱ ምትይው። ግና ኣንድ
ጥያቄ ልጠይቅሽ... ጃንሆይ ኸዝኸ በፊት አላገቡም ነበር እንዴ?”
“አግብተው ነበር እንጂ።”
“እህስ?”
“በእንዴት ያለ ወግ ተጋብተው እሷ የሠርጉ ምሽት እንደ ወጉ ግብር
አብልታ፣ እህል ውሃ ስንኳ ሳትቀምስ በጥኑ ታማ በበነጋው ሞተች።እደብረብርሃን ሥላሤ ነው የተቀበረች፤ ኸዛው እናታቸው ኻሉበት። መርዝ ነው ይላሉ። እንዴት ያለች አለላና ብርቱ ሴት ነበረች አሉ። ደማምና ብርቱ ይሆናቸዋል።”
“እንዴ?” አለች ወለተጊዮርጊስ፣ ሰውነቷን ያልታወቀ ነገር ወረር
አድርጓት። ተነስታ ቆመች። “እኔስ ፈራሁ። እኔንስ በመርዝ ቢገሉኝ?"
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ባህራም
ምጥ
ባህራም በሰኔ ወር የወደቀውን ፈተና እንደገና ለመፈተን
ማጥናት ጀመረ። የራሱ መኝታ ቤት ያረጀና የከረከሰ ሆኖ፣ ደምበኛ ጠረጴዛና ወምበር የለውም፡፡ እዚያ ማጥናት አልቻለም፡፡የዩኒቨርሲቲው ቤተመፃህፍት እየሄደ እንዳያጠና፣ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች ውር ውር እያሉ ሀሳቡን ይሰርቁታል። ከቀኙ፣ ከግራው፣ከፊቱ፣ ከኋላው ደሞ አስር፣ አስራ አምስት ፍራንክ ያበደሩት ሰዎች ያዩታል፣ ይከብዱታል። እነሉልሰገድ ቤት ሄዶ እንዳያጠና ወሬና
ጫጫታ ይበዛል። እኔ ቤት እየመጣ ያጠና ጀመር። ከሰአት በኋላ ሲኒማ እሄድለታለሁ፣ ሲያጠና ይውላል። ማታ እፅፋለሁ ወይም አነባለሁ፣ ሲያጠና ወይም የማኦ ትዜ ቱንግን መፃህፍት ሲያነብ ያመሻል፡፡ ጧት ግን ምንም ያህል አይሰራም፡፡ ወሬ እናበዛለን።
ጧት ገና ከእንቅልፌ ሳልነቃ መጥቶ፣ በቀስታ በሩን ከፍቶ
ገብቶ፣ ጠረጴዛው ዘንድ ተቀምጦ ሲሰራ ይቆያል። ስነቃ “Bon jour
እለዋለሁ። Bon jour ብሎኝ ቡና ይጥድና ስራውን ይቀጥላል።
አልጋዬ ውስጥ እንዳለሁ ትላንት የፃፍኩትን እመለካከታለሁ፤
አርማለሁ፣ እሰርዛለሁ፣ እቀዳለሁ። ሙሉ ሰአት ሲሆን ባህራም «አንድ ጊዜ ዜና ብንሰማ ይረብሽሀል?» ይለኛል፡፡ (የፈረንሳይ ራዲዮ በየሰአቱ አጫጭር ዜና ያሰራጫል) ራስጌዬ ያለችውን ራዲዮ እከፍታታለሁ። ባህራም ያፈላውን ቡና በዱቄት ወተት እየጠጣን ስለቪየትናም ወሬ እንሰማለን። ቪየትኮንግ የደፈጣ አሜሪካኖቹን አጥቅተዋቸው እንደሆን ባህራም ደስ ይለውና ደስታው
አላስጠና ይለዋል። መናገር ይጀምራል።ቬየትኮጎቹ ድል
ማድረጋቸው አይቀርም ይላል፡፡ ንግግሩ ቀስ ብሎ ወደ ኢራን
ይወሳስደዋል።ስለኢራን ሊነግረኝ ይጀምራል። ስለኢራን፣
ስለኮሙኒዝም፣ ስለማኦ ትዜ ቱንግ፣ ስለአሜሪካን ወራሪነትና
አጥቂነት፣ ስለካፒታሊዝም ስናወራ እንቆይና፡ ሙሉ ሰአት ሲደርስ
እንደገና ራዲዮ እንከፍታለን፡፡ ዜናው ያስደስተዋል ወይም
ያበሳጨዋል። ወሬያችንን እንቀጥላለን። የምሳ ሰአት እስኪደርስ እናወራለን፣ እናወራለን ማለት፣ በአብዛኛው እሱ ሲያወራ እኔ አዳምጠዋለሁ፤ እንዳንድ ጊዜ ጥያቄ እጠይቀዋለሁ፡፡ የነገረኝን
እያንዳንዱን ማታ ልተኛ ስል አንድ ትልቅዬ ደብተር ውስጥ አሰፍረው ነበር
አሁን ያንን ደብተር ሳነበው ባህራም ይታየኛል፡፡ እኔ አልጋ
ውስጥ ትራስ ተደግፌ ቁጭ ብዬ፡ እሱ በሽተኛ ሊጠይቅ የመጣ
ይመስል አጠገቤ ወምበር ላይ ተቀምጦ፣ በብልህ ቡናማ አይኖቹ
እያየኝ፣ ፀጉራም እጆቹን በብዙ እያንቀሳቀሰ፣ በወፍራም ልዝብ
ድምፁና በተሰባበረ ፈረንሳይኛው ሲያወራልኝ፣ ቁልጭ ብሎ
ይታየኛል
ወሬው አንድ መስመር ይዞ አይሄድም። ኢራን፣ ኒኮል፣
የባህራም ቤተሰብ፣ የባህራም ጓደኞች፣ ፈረንሳዮች፣ ጥቁሮች፣
ወጣት ኮሙኒስቶች የተባለ የኢራን አገር ማህበር፣ ትምህርት
ቤት፣ ሴቶች፣ ቡሽቲዎች፣ ጋዜጠኞች ብቻ ባህራም ያየውንና
የሰማውን ነገር፣ በህይወቱ የደረሰበትን ወይም በሌሎች ላይ
የደረሰባቸውን ነገር አሳዛኝ ነገር፣ አስደሳች ነገር፣ አስቂኝ ነገር፣
የሆነ ነገር ያወራልኝ ነበር፡፡ ስንቱን ብዬ ልናገረው እችላለሁ?
ጥቂቱን ብቻ ባጭሩ ላስፍረው፣ እንደ ባህራም ካንዱ ወደ ሌላው
እየዘለልኩ. እንደሚከተለው...
አሜሪካኖቹ ይወድቃሉ (ይላል ባህራም) ታያለህ፡፡ ስንቱን ህዝብ
ጨቁነው፣ ስንቱን አገር ፈትፍተው፣ ስንቱን መንግስት ገዝተው
ይችላሉ? አንድ ቀን ይወድቃሉ። እንኳን እንደነሱ ያለ ቂል ፈረስ
ይቅርና፣ እንደ እንግሊዝ ያለ ተንኮለኛ ቀበሮም ወድቋል። ተነስቶ ሌሎች ህዝቦችን
ጨቁኖ መውደቅ የሚቀርለት የለም፡፡ “አሜሪካኖችም ይወድቃሉ፡፡ ይወድቃሉ። ታይቶ የማይታወቅ አወዳደቅ ይወድቃሉ። ያን ጊዜ የአለም ህዝቦች እልል ይላሉ።
በአሜሪካ አግር ተረግጠው ደክመው እልል ለማለት ያህል አቅም ያነሳቸው ደሞ እፎይ ይላሉ
አሜሪካኖቹን መጀመሪያ
ሆ ቺ ሚን ከቪየትናም ያባርራቸዋል::ቀጥሎ እነ ማኦ ሴቱንግ ወይም ወራሾቹ ከሩቅ ምስራቅ ያስወጡዋቸዋል፡፡ ቀጥሎ እንግዲህ ማን ከየት እንደሚያስወጣቸው አላውቅም:: ብቻ እርግጠኛ ነኝ ያስወጡዋቸዋል። ይህን የሰው አገር ደም ጠጥቶ የወፈረ ቂጣቸውን በካልቾ እየመቱ “Yanked go home!
And stay honte!' (ያንኪ ወደ አገርህ ግባ እና እዚያው ቅር!»)
እያሉ ያስወጡዋቸዋል። ከሰው እድሜ በላይ በኖርኩ! አሜሪካ
ስትወድቅ ለማየት እንድችል ብቻ
ምን ማለትህ ነው? ለምን አልጠላቸውም? አሜሪካኖችን ያልጠላሁ ማንን ልጠላ ነው የነፃነትን ዋጋ እያወቅኩ፣ የተጨቆነ ህዝቤን እየወደድኩ፣ አሜሪካኖችን ካልጠላሁማ ሰው አይደለሁም ማለት ነው። ድንጋይ ነኝ ማለት ነው አሜሪካኖች አንድ የተቀደሰ ተግባር አላቸው:: ይኸውም፣ እባብ ያንዲትን ወፍ እንቁላል መጦ ጨርሶ ቅል ብቻ እንደሚያስቀርላት፣እነሱም ያንዲትን አገር ሀብት መጠው ጨርሰው፣ አፈርና ድንጋይ
ይተዉላታል። የኔን አገር ውሰድ። ዋና ሀብቷ ነዳጅ (ፔትሮል
ነው። ነዳጁን ከመሬት መጦ የሚወስደው አሜሪካ ነው
አንድ ቀን ሞሳዴግ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። ተነሳና የኢራን
ሀብት ለኢራን ህዝብ ነው አለ፡፡ አሜሪካኖቹ ተሳስተሀል አሉት፡፡
በቃል ሳይሆን በተግባር፣ የኢራን ሀብት ለአሚሪካ ነው፣ የኢራን
ሀብት ለኢራን ነው ካልክ ኮሙኒስት ነህ ማለት ነው አሉት።
ሲ.አይ.ኤ ልከው ገለበጡት። ሞሳዴግ ተይዞ ሞት ተፈረደበት። ግን ሽማግሌ በመሆኑ፣ የሞት ፍርዱ ወደ እስራት ተሻሻለለት። አሁንም ታስሯል፡፡ የኢራን ሀብት ለአሜሪካኖቹና ለሻህ ነው ያለ ሰው ግን ይሾማል ያሸለማል። ሻህ ማለት በነሲሩስ፣ በነዳርዩሽና በነኻሻር ያዥ ስመ ጥሩ ዙፋን ላይ ተቀምጦ ኢራንን የሚጨቁን ጋንግስተር ማለት ነው:: አጋዦች አሉት። ህዝቡ ያረሰውን ለመንጠቅ የእርሻ ሚኒስትር ያግዘዋል። ህዝቡ ሲነግድ ከነጋዴው ለመቀማት የንግድ ሚኒስትር
ያግዘዋል። ለልዩ ልዩ አይነት ጭቆና ልዩ ልዩ ሚኒስትር አለው።
ህዝቡ በደስታ እንዲጨቆን፣ ማለትም ተጨቆንኩ ብሎ
እንዳያጉረምርም፣ ፀጥ የሚያሰኙ ያገር ግዛትና የፍርድ ሚኒስትሮች
አሉት
ያሻህን ሻህ ሚኒስትሮች፣ በተለይም የውጭ ጉዳይና ያገር ግዛት ሚኒስትሮቹ፣ ትእዛዛቸውን በቀጥታ ከዋሽንግተን ይቀበላሉ።
ምክንያቱም ኢራን የአሜሪካ የነዳጅ ማእድን ናት። ደሞ ኢራን
የሩሲያ ጎረቤት ስለሆነች፣ አሜሪካኖች በጣም ለኢራን
ይጠነቀቁላታል። አንድ ገበሬ ብዙ የምትታለብ ላም ብትኖረው
አይጠነቀቅላትም?
ሻህ ማለት ውሻ ነው፡፡ አሜሪካኖቹ ኢራንን አርደው ብልቷን ሲያወጡ እፉ ምራቅ እየሞላ በአይኑ ይከተላቸዋል፣ ሳምባ ወይም
ሌላ ቁራጭ ስጋ ጣል ያረጉለታል። እሱ ደሞ ህዝቡን ጨቁኖ
ይይዝላቸዋል። አየህ፣ ህዝቡ ተጨቁኖ ካልተያዘ፣ እንደ ሞሳዴግ
ተነስቶ የኢራን ሀብት ለኢራን ሰዎች ይላል። ስለዚህ አሜሪካኖቹ
ለህዝቡ የማይቆረቆር፣ ጥቂት ሚልዮን ብር ቢሰጡት የሚበቃው፣ ህዝቡን ጨቁኖ የሚይዝላቸው ገዥ ይፈልጋሉ፡፡ ለዚህ ነው ዙፋኑን
የሚጠብቁለት በሞሳዴግ ጊዜ ረብሻ ተነሳ፡፡ ሽህ ሽሽቶ ከአገር ወጣ።አሚሪካኖች መጥተወ «የኢራን ሀብት ለኢራን ሰዎች» የሚሉትን የሞሳዴግ ተከታዮች ፈጅተው፣ በዚያውም ያለ የሌለውን ኮሙኒስት አርደው ጨርሰው፣ አገሩን ጸት ካደረጉ በኋላ፣ ና ወደ ዙፋንህ
ተመለስ አሉት፡፡ ወደ ዙፋኑ ተመለሰ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
ባህራም
ምጥ
ባህራም በሰኔ ወር የወደቀውን ፈተና እንደገና ለመፈተን
ማጥናት ጀመረ። የራሱ መኝታ ቤት ያረጀና የከረከሰ ሆኖ፣ ደምበኛ ጠረጴዛና ወምበር የለውም፡፡ እዚያ ማጥናት አልቻለም፡፡የዩኒቨርሲቲው ቤተመፃህፍት እየሄደ እንዳያጠና፣ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች ውር ውር እያሉ ሀሳቡን ይሰርቁታል። ከቀኙ፣ ከግራው፣ከፊቱ፣ ከኋላው ደሞ አስር፣ አስራ አምስት ፍራንክ ያበደሩት ሰዎች ያዩታል፣ ይከብዱታል። እነሉልሰገድ ቤት ሄዶ እንዳያጠና ወሬና
ጫጫታ ይበዛል። እኔ ቤት እየመጣ ያጠና ጀመር። ከሰአት በኋላ ሲኒማ እሄድለታለሁ፣ ሲያጠና ይውላል። ማታ እፅፋለሁ ወይም አነባለሁ፣ ሲያጠና ወይም የማኦ ትዜ ቱንግን መፃህፍት ሲያነብ ያመሻል፡፡ ጧት ግን ምንም ያህል አይሰራም፡፡ ወሬ እናበዛለን።
ጧት ገና ከእንቅልፌ ሳልነቃ መጥቶ፣ በቀስታ በሩን ከፍቶ
ገብቶ፣ ጠረጴዛው ዘንድ ተቀምጦ ሲሰራ ይቆያል። ስነቃ “Bon jour
እለዋለሁ። Bon jour ብሎኝ ቡና ይጥድና ስራውን ይቀጥላል።
አልጋዬ ውስጥ እንዳለሁ ትላንት የፃፍኩትን እመለካከታለሁ፤
አርማለሁ፣ እሰርዛለሁ፣ እቀዳለሁ። ሙሉ ሰአት ሲሆን ባህራም «አንድ ጊዜ ዜና ብንሰማ ይረብሽሀል?» ይለኛል፡፡ (የፈረንሳይ ራዲዮ በየሰአቱ አጫጭር ዜና ያሰራጫል) ራስጌዬ ያለችውን ራዲዮ እከፍታታለሁ። ባህራም ያፈላውን ቡና በዱቄት ወተት እየጠጣን ስለቪየትናም ወሬ እንሰማለን። ቪየትኮንግ የደፈጣ አሜሪካኖቹን አጥቅተዋቸው እንደሆን ባህራም ደስ ይለውና ደስታው
አላስጠና ይለዋል። መናገር ይጀምራል።ቬየትኮጎቹ ድል
ማድረጋቸው አይቀርም ይላል፡፡ ንግግሩ ቀስ ብሎ ወደ ኢራን
ይወሳስደዋል።ስለኢራን ሊነግረኝ ይጀምራል። ስለኢራን፣
ስለኮሙኒዝም፣ ስለማኦ ትዜ ቱንግ፣ ስለአሜሪካን ወራሪነትና
አጥቂነት፣ ስለካፒታሊዝም ስናወራ እንቆይና፡ ሙሉ ሰአት ሲደርስ
እንደገና ራዲዮ እንከፍታለን፡፡ ዜናው ያስደስተዋል ወይም
ያበሳጨዋል። ወሬያችንን እንቀጥላለን። የምሳ ሰአት እስኪደርስ እናወራለን፣ እናወራለን ማለት፣ በአብዛኛው እሱ ሲያወራ እኔ አዳምጠዋለሁ፤ እንዳንድ ጊዜ ጥያቄ እጠይቀዋለሁ፡፡ የነገረኝን
እያንዳንዱን ማታ ልተኛ ስል አንድ ትልቅዬ ደብተር ውስጥ አሰፍረው ነበር
አሁን ያንን ደብተር ሳነበው ባህራም ይታየኛል፡፡ እኔ አልጋ
ውስጥ ትራስ ተደግፌ ቁጭ ብዬ፡ እሱ በሽተኛ ሊጠይቅ የመጣ
ይመስል አጠገቤ ወምበር ላይ ተቀምጦ፣ በብልህ ቡናማ አይኖቹ
እያየኝ፣ ፀጉራም እጆቹን በብዙ እያንቀሳቀሰ፣ በወፍራም ልዝብ
ድምፁና በተሰባበረ ፈረንሳይኛው ሲያወራልኝ፣ ቁልጭ ብሎ
ይታየኛል
ወሬው አንድ መስመር ይዞ አይሄድም። ኢራን፣ ኒኮል፣
የባህራም ቤተሰብ፣ የባህራም ጓደኞች፣ ፈረንሳዮች፣ ጥቁሮች፣
ወጣት ኮሙኒስቶች የተባለ የኢራን አገር ማህበር፣ ትምህርት
ቤት፣ ሴቶች፣ ቡሽቲዎች፣ ጋዜጠኞች ብቻ ባህራም ያየውንና
የሰማውን ነገር፣ በህይወቱ የደረሰበትን ወይም በሌሎች ላይ
የደረሰባቸውን ነገር አሳዛኝ ነገር፣ አስደሳች ነገር፣ አስቂኝ ነገር፣
የሆነ ነገር ያወራልኝ ነበር፡፡ ስንቱን ብዬ ልናገረው እችላለሁ?
ጥቂቱን ብቻ ባጭሩ ላስፍረው፣ እንደ ባህራም ካንዱ ወደ ሌላው
እየዘለልኩ. እንደሚከተለው...
አሜሪካኖቹ ይወድቃሉ (ይላል ባህራም) ታያለህ፡፡ ስንቱን ህዝብ
ጨቁነው፣ ስንቱን አገር ፈትፍተው፣ ስንቱን መንግስት ገዝተው
ይችላሉ? አንድ ቀን ይወድቃሉ። እንኳን እንደነሱ ያለ ቂል ፈረስ
ይቅርና፣ እንደ እንግሊዝ ያለ ተንኮለኛ ቀበሮም ወድቋል። ተነስቶ ሌሎች ህዝቦችን
ጨቁኖ መውደቅ የሚቀርለት የለም፡፡ “አሜሪካኖችም ይወድቃሉ፡፡ ይወድቃሉ። ታይቶ የማይታወቅ አወዳደቅ ይወድቃሉ። ያን ጊዜ የአለም ህዝቦች እልል ይላሉ።
በአሜሪካ አግር ተረግጠው ደክመው እልል ለማለት ያህል አቅም ያነሳቸው ደሞ እፎይ ይላሉ
አሜሪካኖቹን መጀመሪያ
ሆ ቺ ሚን ከቪየትናም ያባርራቸዋል::ቀጥሎ እነ ማኦ ሴቱንግ ወይም ወራሾቹ ከሩቅ ምስራቅ ያስወጡዋቸዋል፡፡ ቀጥሎ እንግዲህ ማን ከየት እንደሚያስወጣቸው አላውቅም:: ብቻ እርግጠኛ ነኝ ያስወጡዋቸዋል። ይህን የሰው አገር ደም ጠጥቶ የወፈረ ቂጣቸውን በካልቾ እየመቱ “Yanked go home!
And stay honte!' (ያንኪ ወደ አገርህ ግባ እና እዚያው ቅር!»)
እያሉ ያስወጡዋቸዋል። ከሰው እድሜ በላይ በኖርኩ! አሜሪካ
ስትወድቅ ለማየት እንድችል ብቻ
ምን ማለትህ ነው? ለምን አልጠላቸውም? አሜሪካኖችን ያልጠላሁ ማንን ልጠላ ነው የነፃነትን ዋጋ እያወቅኩ፣ የተጨቆነ ህዝቤን እየወደድኩ፣ አሜሪካኖችን ካልጠላሁማ ሰው አይደለሁም ማለት ነው። ድንጋይ ነኝ ማለት ነው አሜሪካኖች አንድ የተቀደሰ ተግባር አላቸው:: ይኸውም፣ እባብ ያንዲትን ወፍ እንቁላል መጦ ጨርሶ ቅል ብቻ እንደሚያስቀርላት፣እነሱም ያንዲትን አገር ሀብት መጠው ጨርሰው፣ አፈርና ድንጋይ
ይተዉላታል። የኔን አገር ውሰድ። ዋና ሀብቷ ነዳጅ (ፔትሮል
ነው። ነዳጁን ከመሬት መጦ የሚወስደው አሜሪካ ነው
አንድ ቀን ሞሳዴግ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። ተነሳና የኢራን
ሀብት ለኢራን ህዝብ ነው አለ፡፡ አሜሪካኖቹ ተሳስተሀል አሉት፡፡
በቃል ሳይሆን በተግባር፣ የኢራን ሀብት ለአሚሪካ ነው፣ የኢራን
ሀብት ለኢራን ነው ካልክ ኮሙኒስት ነህ ማለት ነው አሉት።
ሲ.አይ.ኤ ልከው ገለበጡት። ሞሳዴግ ተይዞ ሞት ተፈረደበት። ግን ሽማግሌ በመሆኑ፣ የሞት ፍርዱ ወደ እስራት ተሻሻለለት። አሁንም ታስሯል፡፡ የኢራን ሀብት ለአሜሪካኖቹና ለሻህ ነው ያለ ሰው ግን ይሾማል ያሸለማል። ሻህ ማለት በነሲሩስ፣ በነዳርዩሽና በነኻሻር ያዥ ስመ ጥሩ ዙፋን ላይ ተቀምጦ ኢራንን የሚጨቁን ጋንግስተር ማለት ነው:: አጋዦች አሉት። ህዝቡ ያረሰውን ለመንጠቅ የእርሻ ሚኒስትር ያግዘዋል። ህዝቡ ሲነግድ ከነጋዴው ለመቀማት የንግድ ሚኒስትር
ያግዘዋል። ለልዩ ልዩ አይነት ጭቆና ልዩ ልዩ ሚኒስትር አለው።
ህዝቡ በደስታ እንዲጨቆን፣ ማለትም ተጨቆንኩ ብሎ
እንዳያጉረምርም፣ ፀጥ የሚያሰኙ ያገር ግዛትና የፍርድ ሚኒስትሮች
አሉት
ያሻህን ሻህ ሚኒስትሮች፣ በተለይም የውጭ ጉዳይና ያገር ግዛት ሚኒስትሮቹ፣ ትእዛዛቸውን በቀጥታ ከዋሽንግተን ይቀበላሉ።
ምክንያቱም ኢራን የአሜሪካ የነዳጅ ማእድን ናት። ደሞ ኢራን
የሩሲያ ጎረቤት ስለሆነች፣ አሜሪካኖች በጣም ለኢራን
ይጠነቀቁላታል። አንድ ገበሬ ብዙ የምትታለብ ላም ብትኖረው
አይጠነቀቅላትም?
ሻህ ማለት ውሻ ነው፡፡ አሜሪካኖቹ ኢራንን አርደው ብልቷን ሲያወጡ እፉ ምራቅ እየሞላ በአይኑ ይከተላቸዋል፣ ሳምባ ወይም
ሌላ ቁራጭ ስጋ ጣል ያረጉለታል። እሱ ደሞ ህዝቡን ጨቁኖ
ይይዝላቸዋል። አየህ፣ ህዝቡ ተጨቁኖ ካልተያዘ፣ እንደ ሞሳዴግ
ተነስቶ የኢራን ሀብት ለኢራን ሰዎች ይላል። ስለዚህ አሜሪካኖቹ
ለህዝቡ የማይቆረቆር፣ ጥቂት ሚልዮን ብር ቢሰጡት የሚበቃው፣ ህዝቡን ጨቁኖ የሚይዝላቸው ገዥ ይፈልጋሉ፡፡ ለዚህ ነው ዙፋኑን
የሚጠብቁለት በሞሳዴግ ጊዜ ረብሻ ተነሳ፡፡ ሽህ ሽሽቶ ከአገር ወጣ።አሚሪካኖች መጥተወ «የኢራን ሀብት ለኢራን ሰዎች» የሚሉትን የሞሳዴግ ተከታዮች ፈጅተው፣ በዚያውም ያለ የሌለውን ኮሙኒስት አርደው ጨርሰው፣ አገሩን ጸት ካደረጉ በኋላ፣ ና ወደ ዙፋንህ
ተመለስ አሉት፡፡ ወደ ዙፋኑ ተመለሰ
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
ዉሃ ሆንሁ፣ የመጨረሻዉን ድንጋጤ ደነገጥሁ።
ከነበርሁበት የምድር በታቹ የሲራክ ፯ ማዕከል ወጥቼ በቅርበት ወደሚገኘዉ የድንግል ማርያም ገዳም ለጸሎት ገባሁ አንድ ያለኝ አቅም ጸሎት ነዉና፣ አሳፍሮኝ የማያዉቀዉን አምላክ በእናትህ እርዳኝ አልሁት ተንበርክኬ ከተንበረከክሁበት ተነስቼ በምሥራቅ በኩል ባለዉ የቅጽሩ
በር ልወጣ እየተራመድሁ ልክ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ላይ ስደርስ፣ ደስ የሚያሰኝ የሕጻናት መዝሙር በጆሮዬ ጥልቅ አለ በክፍቱ መስኮት አስግጌ ወደ ዉስጥ ስመለከት፣ ሰልፍና ልብሳቸዉን ያሳመሩ ሕጻናት “ሀገሪትነ” የሚለዉን ነባር ዝማሬ በኅብረት ያጠናሉ። ለአጭር
አፍታ ከዝማሬያቸዉ ቀምሼ መንገዴን ልቀጥል እግሬን ሳነሳ አንድ በየት
በኩል እንደ መጣ ያላየሁት፤ 'ቤ መ' የሚል ኮድ ያለዉ ታርጋ የለጠፈ
መኪና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በር ጥሩንባዉን ነፋና ሲጢጥ ብሎ ቆመ። የታርጋዉ ኮድ ትኩረቴን ስለ ሳበዉ፣ በአዳራሹ እና በግቢዉ አጥር መካከል ወዳለዉ ሰዋራ ሥፍራ ተሰዉሬ የሚሆነዉን ሁሉ በሥርቆሽ መከታተሌን ጀመርሁ: አፍታም ሳትቆይ፣ ሕጻናቱን
እያስጠናች የነበረችዋ ወጣት ወደ በሩ ብቅ ብላ አየችዉና ልጆቹን
እንዲወጡ ጠራቻቸዉ። ሕጻናቱም በደስታ እየፈነደቁ ተሯሩጠዉ ወጥተዉ የመኪናዉ በር እስከሚከፈትላቸዉ ድረስ ተቁነጠነጡ።
“ኧረ ክፈቱልን” ይላል አንደኛዉ ሕጻን፣ አላዳርስ ብሎት በሩን ራሱ
ለመክፈት እየታገለ
“ስሚ ለማን እንደምዘምር አዉቀሻል ግን? ለመንግሥት እኮ ነዉ” ትላለች ሌላኘዋ ጓደኛዋን ለማስቀናት በሚመስል አኳኋን አንገቷን እየወዘወዘች።
“ለመግሥት? ኧረ አይባልም!” ብላ አረመቻት ያቺኛዋ፣ በሳቅ ቡፍ
እያለችባት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም ጠርታ፣ መንግሥት ያለችዋን ልጅ አላገጠችባት።
አሁን ነዉ እንግዲህ መፍጠን አልሁት ለራሴ፡ ዕድሎች ከስንት አንድ
ከላይ ይወርዱልናል፣ አብዛኞቻችን ግን ራሳችን ነን የፈጠርናቸዉ› ሲባል
ሰምቼ ነበር በማዕከላችን በሲራክ ፯ ከስንት አንድ ከሚወርዱት ዕድሎች
አንደኛዉ ይኼዉ የዓይኔ ብረቱ ሥር ወርዶልኛል።
እንዴት ብጠቀመዉ ይሻላል?
ሁሉም ሕጻናት ከወጡ በኋላ መዝሙሩን ያስጠናችዋ ወጣት መብራቱን
አጠፋፍታ ነጠላዋንም በቅጡ እያጣፋች መጣች፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ሾፌሩ
አልወረደም አለመዉረዱ ሲገርመኝ፤ በሩንም ራሷ እንድትከፍትላቸዉ
ጠበቃት እሷ ደርሳ ስትከፍትላቸዉ ልጆቹ እሽቅድምድም ፈጥረዉ አይገቡ የለም እርስ በእርስ እየተጣጣሉ ገቡ፡ አሁን መኪናዉ ፊቱን አዙሮ ይሄዳል ብዬ ስጠባበቅ፣ ምን እንደ ረሳች እንጃላት፣ አስጠኛቸዉ ወረደችና ተመልሳ ወደ አዳራሹ ሮጣ ገባች። ይኸኔ ጥግ ለጥግ
ተሹለኩልኬ የአዳራሹን የኋላ በር በኃይል አንኳኳሁባት። ያለ ምንም ፋታ ደጋግሜ ሳንጓጓባት ብልጭ ብሎባት በእልህ ከፈተችልኝ።
“እ! ምንድነዉ?” አለች፣ በሩን በጥድፊያ ስትከፍተዉ እኔ በድንግዝግዙ
ዉስጥ ብቁለጨለጭባት የተመለሰችዉ ከበሮዉን ረስታዉ ኖሯል ለካ፣
በቀኝ ትከሻዋ አንግታዋለች ለኹለት ሰዓታት ሰመመን ዉስጥ የሚከተዉን ቅባት የረጨሁባቸዉ መዳፎቼን እያፋተግሁ ትንሽ የመዘናጊያ ፋታ ከሰጠኋት በኋላ ዘልዬ አፏን አፈንሁት፡ በቅጽበት መዝለፍለፍ ስትጀመርልኝ፤ ከበሮዉን በአንድ እጄ፣ እሷን ደግሞ
በሌላኛዉ እጄ ለመደገፍ ሞከርሁ፡ ሽርተት ብላ መሬት ያዘችልኝ፡ ዝቅ ብዬ እጄን በመሬቱ አሽቼ ቅባቱን ካረከስሁት በኋላ፣ ነጠላዋን ልክ እሷ ተከናንባዉ እንደነበር አድርጌ አጣፋሁትና ከበሮዉን አንስቼ አነገትሁት ክራሬንም በግራ እጄ አንጠለጠልሁትና መብራቱን አጠፋፋሁ፡፡
መኪናዉም ፊቱን አዙሮ ለመሄድ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቀኝ፡ ከሾፌሩ ይልቅ ሕጻናቱ እንዳይለዩኝ የባሰ ስለ ሰጋሁ፣ ከበሮዉን ከኋላ ጭኜ፣ ጋቢና ገባሁ ብቻ የፈራሁትን ያህል ሳልቸገር፣ ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት ገባሁ የመኪና ማቆሚያዉ ላይ ስንደርስ፣ ሌላ ሰዉ ተቀብሎን ወደ
ግብዣዉ አዳራሽ ወሰደን በዚያ ስንደርስ ደግሞ አንዲት ባህላዊ ቀሚስ
የለበስች ሴት ተቀብላ ከመድረኩ ጀርባ ካሉት ክፍሎች ወደ አንደኛዉ
አስገባችን ክፍሉን ሳየዉ ጠበብ ያለ ቢመስለኝም፣ ስንገባበት ግን ጠብ
እንኳን አላልንበትም ሌላ ብዙ ሰዉ ቢጨመር ሁሉ አይጠብም፡ በዚያም
ላይ የመድረኩን ትዕይንት በቀጥታ የሚያስተላልፍልን ዘመናዊ
ቴሌቪዥን ግድግዳዉ ላይ ተሰቅሎበታል
አሁን ነዉ ጉዱ ከሕጻናቱ ጋር በደማቅ ብርሃን ልፋጠጥ ነዉ፡ መቼም ጥያቄ
መጠየቃቸዉ አይቀር፣ ወይ ደግሞ እንድናገር የሚያደርጉበት አንድ ነገር
አያጡም: ያስጠናቻቸዉ ወጣት እንዳልሆንሁ ሲያዉቁ ምን ያደርጉ
ይሆን? በተቻለኝ መጠን አንገቴን አቀርቅሬ ወዲያ ወዲህ እያልሁ ራሴን ባተሌ አደረግሁባቸዉ። ዓይናቸዉ ዉስጥ ላለመግባት ብዙ ተፍተለተልሁ መቆያ ክፍል የሰጠችን ደርባባ ሴት ተመልሳ መጣችና የመርሐ ግብሩ ቅደም ተከተል የሰፈረበት ወረቀት ሰጠችኝ፡ አስከትላም፣
የኛ ተራ እስከሚደርስ ድረስ የመጨረሻ ልምምድ ማድረግ ከፈለግን፣
ያለንበት ክፍል ድምፅ ወደ ዉጪ ስለማያስወጣ እዚሁ መለማመድ
እንደምንችል አሳወቀችኝ፡ ስለዚያ ገና ሳላመሰግናት፣ መቆያ ምግብ
እንድናዝዝ ጎንበስ ብላ ጠየቀችን፡ እንዲህ ያለችዋ ሽቁጥቁጥ ሴት ለሕጻናቱ ከተመደበች፣ ለዋናዎቹ እንግዶችማ እንዴት ያለ ሰዉ ሊመደብ እንደሚችል ገመትሁ። መቼም ትሕትናዋ ወደር አይገኝለትም: ምንም እንኳን ሕጻናቱ ምርጫቸዉን እየለዋወጡ ረዥም ሰዓት ቢወስዱባትም፣ከበሬታዋ ግን አልቀነስም፡ እኔም እንዲሁ ወዳፌ የመጣልኝን የባቄላ
ሾርባ አዘዝሁ።
የሕጻናቱን መዝሙር ተከትሎ መንዙማ የሚያቀርቡ ሙስሊም ሕጻናትም መኖራቸዉን ያወቅሁት ወረቀቱ ላይ የሰፈረዉን ዝርዝር መርሐ ግብር ከተመለከትሁ በኋላ ነበር ሰዓቴን ስመለhት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ይላል። በዕቅዱ መሠረት መዝሙር ለሚቀርብበት ተራ፣ ሃያ ደቂቃዎች ይቀራሉ ማለት ነዉ: ከፊቴ የተሰቀለዉ ቴሌቪዥን፣
የአዳራሹን ትዕይንት ቀጥታ እያመጣ ስለሚያሳየኝ፣ የተጠቀሱት መርሐ
ግብራት ያለ ምንም መጓተት በየተራቸዉ እየቀረቡ መሆኑን አዉቄያለሁ:
ሲንሾካሾኩ ሰምቼ በቀስታ ዞር ብል ሁሉም ሕጻናት አፍጥጠዉብኛል ዝምታየ ሽሽቴ፣ አድራጎቴ ሁሉ ገርሟቸዉ! ወዲያ ስልም ወዲህም ስል በዓይናቸዉ ይከታተሉኛል። የመጣዉ ይምጣ ብዬ ክንብንቤን ገለጥ
አደረግሁና፤ ማንነቴን በከፊል ነገርኋቸዉ።
“እንዴ?” ተባባሉ
“አላልኋችሁም? እግዚሐርያ አይደለችም” አለ አንደኛዉ ሕጻን፣ዉርርዱን በማሸነፍ።
“እሷስ?”
“እግዚሐርያስ?”
"በጥያቄ አካለቡኝ"
“እግዚሐርያ እኮ ድገት አሟት ተተኪልኝ ብላኝ ነዉ” አልኋቸዉ፣ መዝሙሩን ያስጠናቻቸዉ ልጅ እግዚሐርያ መባሏን ከራሳቸዉ አፍ ስላወቅሁ ስሟን መጥራቴ ለአመኔታ እንደሚያግዘኝ በማሰብ
“ኧረ ቅድም ደህና አልነበረች? ከምኔዉ አመማት?” አለ፣ ከመካከላቸዉ
ቅድም ጀምሮ ቀደም ቀደም የሚለዉ ልጅ።
“ግድየለምቆይ፤ በኋላ በስልክ አገናኛችኋለሁ: አሁን መዝሙሩን
ለመጨረሻ ጊዜ እንለማመደዉ? የማቅረቢያ ሰዓታችን እየደረሰ ነዉ። በሉ
ተነሱ። ተነሷ” አልሁ በመለማመጥም በማጣደፍም ጭምር፣ ከዚህ በላይ
እንዳይከራከሩኝ በልቤ እየጸልይሁ፡ ክራሬን እየቃኘሁ “በሉ እሺ፤
መዝሙሩን ለመዘመር፣ በአብ በወልድ በመፈስ ቅዱስ ስም…”አልኋቸዉ፣ ፋታ ላለመስጠት እዉነትም አላሳፈሩኝም፤ ብድግ ብድግ አሉልኝ፡ ከመካከላቸዉ ትንሽ ከፍ የምትለዋ ልጅ ከበሮዉን አነሳች፡ እኔም መዝሙሩን በቅጡ የምችለዉ ስለሆነ፣ እምብዛም
ሳልደነቃቀፍባቸዉ ጥሩ አድርገን አብረን ወጣነዉ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
ዉሃ ሆንሁ፣ የመጨረሻዉን ድንጋጤ ደነገጥሁ።
ከነበርሁበት የምድር በታቹ የሲራክ ፯ ማዕከል ወጥቼ በቅርበት ወደሚገኘዉ የድንግል ማርያም ገዳም ለጸሎት ገባሁ አንድ ያለኝ አቅም ጸሎት ነዉና፣ አሳፍሮኝ የማያዉቀዉን አምላክ በእናትህ እርዳኝ አልሁት ተንበርክኬ ከተንበረከክሁበት ተነስቼ በምሥራቅ በኩል ባለዉ የቅጽሩ
በር ልወጣ እየተራመድሁ ልክ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ ላይ ስደርስ፣ ደስ የሚያሰኝ የሕጻናት መዝሙር በጆሮዬ ጥልቅ አለ በክፍቱ መስኮት አስግጌ ወደ ዉስጥ ስመለከት፣ ሰልፍና ልብሳቸዉን ያሳመሩ ሕጻናት “ሀገሪትነ” የሚለዉን ነባር ዝማሬ በኅብረት ያጠናሉ። ለአጭር
አፍታ ከዝማሬያቸዉ ቀምሼ መንገዴን ልቀጥል እግሬን ሳነሳ አንድ በየት
በኩል እንደ መጣ ያላየሁት፤ 'ቤ መ' የሚል ኮድ ያለዉ ታርጋ የለጠፈ
መኪና ከሰንበት ትምህርት ቤቱ አዳራሽ በር ጥሩንባዉን ነፋና ሲጢጥ ብሎ ቆመ። የታርጋዉ ኮድ ትኩረቴን ስለ ሳበዉ፣ በአዳራሹ እና በግቢዉ አጥር መካከል ወዳለዉ ሰዋራ ሥፍራ ተሰዉሬ የሚሆነዉን ሁሉ በሥርቆሽ መከታተሌን ጀመርሁ: አፍታም ሳትቆይ፣ ሕጻናቱን
እያስጠናች የነበረችዋ ወጣት ወደ በሩ ብቅ ብላ አየችዉና ልጆቹን
እንዲወጡ ጠራቻቸዉ። ሕጻናቱም በደስታ እየፈነደቁ ተሯሩጠዉ ወጥተዉ የመኪናዉ በር እስከሚከፈትላቸዉ ድረስ ተቁነጠነጡ።
“ኧረ ክፈቱልን” ይላል አንደኛዉ ሕጻን፣ አላዳርስ ብሎት በሩን ራሱ
ለመክፈት እየታገለ
“ስሚ ለማን እንደምዘምር አዉቀሻል ግን? ለመንግሥት እኮ ነዉ” ትላለች ሌላኘዋ ጓደኛዋን ለማስቀናት በሚመስል አኳኋን አንገቷን እየወዘወዘች።
“ለመግሥት? ኧረ አይባልም!” ብላ አረመቻት ያቺኛዋ፣ በሳቅ ቡፍ
እያለችባት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም ጠርታ፣ መንግሥት ያለችዋን ልጅ አላገጠችባት።
አሁን ነዉ እንግዲህ መፍጠን አልሁት ለራሴ፡ ዕድሎች ከስንት አንድ
ከላይ ይወርዱልናል፣ አብዛኞቻችን ግን ራሳችን ነን የፈጠርናቸዉ› ሲባል
ሰምቼ ነበር በማዕከላችን በሲራክ ፯ ከስንት አንድ ከሚወርዱት ዕድሎች
አንደኛዉ ይኼዉ የዓይኔ ብረቱ ሥር ወርዶልኛል።
እንዴት ብጠቀመዉ ይሻላል?
ሁሉም ሕጻናት ከወጡ በኋላ መዝሙሩን ያስጠናችዋ ወጣት መብራቱን
አጠፋፍታ ነጠላዋንም በቅጡ እያጣፋች መጣች፡ ይኼ ሁሉ ሲሆን ሾፌሩ
አልወረደም አለመዉረዱ ሲገርመኝ፤ በሩንም ራሷ እንድትከፍትላቸዉ
ጠበቃት እሷ ደርሳ ስትከፍትላቸዉ ልጆቹ እሽቅድምድም ፈጥረዉ አይገቡ የለም እርስ በእርስ እየተጣጣሉ ገቡ፡ አሁን መኪናዉ ፊቱን አዙሮ ይሄዳል ብዬ ስጠባበቅ፣ ምን እንደ ረሳች እንጃላት፣ አስጠኛቸዉ ወረደችና ተመልሳ ወደ አዳራሹ ሮጣ ገባች። ይኸኔ ጥግ ለጥግ
ተሹለኩልኬ የአዳራሹን የኋላ በር በኃይል አንኳኳሁባት። ያለ ምንም ፋታ ደጋግሜ ሳንጓጓባት ብልጭ ብሎባት በእልህ ከፈተችልኝ።
“እ! ምንድነዉ?” አለች፣ በሩን በጥድፊያ ስትከፍተዉ እኔ በድንግዝግዙ
ዉስጥ ብቁለጨለጭባት የተመለሰችዉ ከበሮዉን ረስታዉ ኖሯል ለካ፣
በቀኝ ትከሻዋ አንግታዋለች ለኹለት ሰዓታት ሰመመን ዉስጥ የሚከተዉን ቅባት የረጨሁባቸዉ መዳፎቼን እያፋተግሁ ትንሽ የመዘናጊያ ፋታ ከሰጠኋት በኋላ ዘልዬ አፏን አፈንሁት፡ በቅጽበት መዝለፍለፍ ስትጀመርልኝ፤ ከበሮዉን በአንድ እጄ፣ እሷን ደግሞ
በሌላኛዉ እጄ ለመደገፍ ሞከርሁ፡ ሽርተት ብላ መሬት ያዘችልኝ፡ ዝቅ ብዬ እጄን በመሬቱ አሽቼ ቅባቱን ካረከስሁት በኋላ፣ ነጠላዋን ልክ እሷ ተከናንባዉ እንደነበር አድርጌ አጣፋሁትና ከበሮዉን አንስቼ አነገትሁት ክራሬንም በግራ እጄ አንጠለጠልሁትና መብራቱን አጠፋፋሁ፡፡
መኪናዉም ፊቱን አዙሮ ለመሄድ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቀኝ፡ ከሾፌሩ ይልቅ ሕጻናቱ እንዳይለዩኝ የባሰ ስለ ሰጋሁ፣ ከበሮዉን ከኋላ ጭኜ፣ ጋቢና ገባሁ ብቻ የፈራሁትን ያህል ሳልቸገር፣ ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት ገባሁ የመኪና ማቆሚያዉ ላይ ስንደርስ፣ ሌላ ሰዉ ተቀብሎን ወደ
ግብዣዉ አዳራሽ ወሰደን በዚያ ስንደርስ ደግሞ አንዲት ባህላዊ ቀሚስ
የለበስች ሴት ተቀብላ ከመድረኩ ጀርባ ካሉት ክፍሎች ወደ አንደኛዉ
አስገባችን ክፍሉን ሳየዉ ጠበብ ያለ ቢመስለኝም፣ ስንገባበት ግን ጠብ
እንኳን አላልንበትም ሌላ ብዙ ሰዉ ቢጨመር ሁሉ አይጠብም፡ በዚያም
ላይ የመድረኩን ትዕይንት በቀጥታ የሚያስተላልፍልን ዘመናዊ
ቴሌቪዥን ግድግዳዉ ላይ ተሰቅሎበታል
አሁን ነዉ ጉዱ ከሕጻናቱ ጋር በደማቅ ብርሃን ልፋጠጥ ነዉ፡ መቼም ጥያቄ
መጠየቃቸዉ አይቀር፣ ወይ ደግሞ እንድናገር የሚያደርጉበት አንድ ነገር
አያጡም: ያስጠናቻቸዉ ወጣት እንዳልሆንሁ ሲያዉቁ ምን ያደርጉ
ይሆን? በተቻለኝ መጠን አንገቴን አቀርቅሬ ወዲያ ወዲህ እያልሁ ራሴን ባተሌ አደረግሁባቸዉ። ዓይናቸዉ ዉስጥ ላለመግባት ብዙ ተፍተለተልሁ መቆያ ክፍል የሰጠችን ደርባባ ሴት ተመልሳ መጣችና የመርሐ ግብሩ ቅደም ተከተል የሰፈረበት ወረቀት ሰጠችኝ፡ አስከትላም፣
የኛ ተራ እስከሚደርስ ድረስ የመጨረሻ ልምምድ ማድረግ ከፈለግን፣
ያለንበት ክፍል ድምፅ ወደ ዉጪ ስለማያስወጣ እዚሁ መለማመድ
እንደምንችል አሳወቀችኝ፡ ስለዚያ ገና ሳላመሰግናት፣ መቆያ ምግብ
እንድናዝዝ ጎንበስ ብላ ጠየቀችን፡ እንዲህ ያለችዋ ሽቁጥቁጥ ሴት ለሕጻናቱ ከተመደበች፣ ለዋናዎቹ እንግዶችማ እንዴት ያለ ሰዉ ሊመደብ እንደሚችል ገመትሁ። መቼም ትሕትናዋ ወደር አይገኝለትም: ምንም እንኳን ሕጻናቱ ምርጫቸዉን እየለዋወጡ ረዥም ሰዓት ቢወስዱባትም፣ከበሬታዋ ግን አልቀነስም፡ እኔም እንዲሁ ወዳፌ የመጣልኝን የባቄላ
ሾርባ አዘዝሁ።
የሕጻናቱን መዝሙር ተከትሎ መንዙማ የሚያቀርቡ ሙስሊም ሕጻናትም መኖራቸዉን ያወቅሁት ወረቀቱ ላይ የሰፈረዉን ዝርዝር መርሐ ግብር ከተመለከትሁ በኋላ ነበር ሰዓቴን ስመለhት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ይላል። በዕቅዱ መሠረት መዝሙር ለሚቀርብበት ተራ፣ ሃያ ደቂቃዎች ይቀራሉ ማለት ነዉ: ከፊቴ የተሰቀለዉ ቴሌቪዥን፣
የአዳራሹን ትዕይንት ቀጥታ እያመጣ ስለሚያሳየኝ፣ የተጠቀሱት መርሐ
ግብራት ያለ ምንም መጓተት በየተራቸዉ እየቀረቡ መሆኑን አዉቄያለሁ:
ሲንሾካሾኩ ሰምቼ በቀስታ ዞር ብል ሁሉም ሕጻናት አፍጥጠዉብኛል ዝምታየ ሽሽቴ፣ አድራጎቴ ሁሉ ገርሟቸዉ! ወዲያ ስልም ወዲህም ስል በዓይናቸዉ ይከታተሉኛል። የመጣዉ ይምጣ ብዬ ክንብንቤን ገለጥ
አደረግሁና፤ ማንነቴን በከፊል ነገርኋቸዉ።
“እንዴ?” ተባባሉ
“አላልኋችሁም? እግዚሐርያ አይደለችም” አለ አንደኛዉ ሕጻን፣ዉርርዱን በማሸነፍ።
“እሷስ?”
“እግዚሐርያስ?”
"በጥያቄ አካለቡኝ"
“እግዚሐርያ እኮ ድገት አሟት ተተኪልኝ ብላኝ ነዉ” አልኋቸዉ፣ መዝሙሩን ያስጠናቻቸዉ ልጅ እግዚሐርያ መባሏን ከራሳቸዉ አፍ ስላወቅሁ ስሟን መጥራቴ ለአመኔታ እንደሚያግዘኝ በማሰብ
“ኧረ ቅድም ደህና አልነበረች? ከምኔዉ አመማት?” አለ፣ ከመካከላቸዉ
ቅድም ጀምሮ ቀደም ቀደም የሚለዉ ልጅ።
“ግድየለምቆይ፤ በኋላ በስልክ አገናኛችኋለሁ: አሁን መዝሙሩን
ለመጨረሻ ጊዜ እንለማመደዉ? የማቅረቢያ ሰዓታችን እየደረሰ ነዉ። በሉ
ተነሱ። ተነሷ” አልሁ በመለማመጥም በማጣደፍም ጭምር፣ ከዚህ በላይ
እንዳይከራከሩኝ በልቤ እየጸልይሁ፡ ክራሬን እየቃኘሁ “በሉ እሺ፤
መዝሙሩን ለመዘመር፣ በአብ በወልድ በመፈስ ቅዱስ ስም…”አልኋቸዉ፣ ፋታ ላለመስጠት እዉነትም አላሳፈሩኝም፤ ብድግ ብድግ አሉልኝ፡ ከመካከላቸዉ ትንሽ ከፍ የምትለዋ ልጅ ከበሮዉን አነሳች፡ እኔም መዝሙሩን በቅጡ የምችለዉ ስለሆነ፣ እምብዛም
ሳልደነቃቀፍባቸዉ ጥሩ አድርገን አብረን ወጣነዉ
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...የሚስተር ኬን የሙዚቃ ትርዒት ሀሙስ ታይቶ ሲያበቃ ሎርድ ማውንት ስቨርን ቅዳሜውን ከኢስት ሊን ጓዙን ጠቅልሎ ለመነሳት አቀደ የጉዞው ዝግጅትም አስቀድሞ ተጀመረ ነግር ግን ቀኑ ከይረሰ በኋላ ያ ሁሉ የመነሳት ዝግጅት ለሁለተኛ ጊዜ እንዳይሰናከል አጠራጣሪ መስሎ ታየ ገና ሲነጋ ቤቱ ተሸበረ ከዌስትሊን ቀዶ ጠጋኝ ሐኪም ሚስተር ዌይን ራይት ተጠርቶሰ ከኧፕርሎ መኝታ ቤት
ገባ " ኧሮሎ አሁንም በሽታው እንደገና ክፉኛ ተቀሰቀሰበትና በጣም ተበሳጨ።
« በዚህ ዐይነት ገና ሳምንት ሁለት ሳምንት ወይም አንድ ወር እዚህ እቆይ ይሆናል » አላት ለሳቤላ ።
« በጣም አዝናለሁ... አባባ ኤስት ሊንን በጣም ስልችኸዋል " »
« መሰልቸት ይደለም ። ከኢስትሊን እንድወጣ የምፈልግበት ሌሎች ምክንያቶች አሉኝ አሁን ኮ አንቺም ወደ ሙዚቃ ትርዒት መሔድ ላትችይ ነው »
ሳቤላ ፊቷ ቀላ ። ምነው አባባ ? ላትችይ ነው አልከኝ?»
«አዎን ማን ይዞሽ ይሔዳል ? እኔ እንደ ሆንኩ ከመኝታዬ እንኳን መነሣት አልቻልኩም »
« መገኘት አለብኝ . . . አባባ " አለዚያማ እንግኛለን ብለን አስወርተን ብንቀር ዱሮውንም እንደማናደርገው አወቀን ያስወራነው ይመስልብናል " ደግሞ እንደምታውቀው ከዱሲ ቤተሰብ ጋር እዚያ ለመናኘት †ቃጥረናል " ባይሆን ሠረገላው እዚያው ያድርሰኝና እኔ ከነሱ ጋር እገባለሁ" »
« በይ እሺ ላንቺ ደስ እንዲለሽ እኔ እንኳን የምትቀሪበትን ስበብ ካገኘሽ እንዳጋጣ ቀርተሽ የምትጠቀሚበት መስሎኝ ነበር » አላት "
« በጭራሽ ! እኔ ሚስተር ኬንን ከነሙዚቃው የማልንቀው መሆኔን ዌስት ሊን እንዲያይ እፈልጋለሁ » አለች ሳቤላ እየሣቀች ።
ቀን ላይ የዊልያም ቬን በሽታ በጣም ከሚያሳስብ ደረጃ ላይ ደረሰ " ስቃዩ በጣም የሚያሰቅቅና የሚያስጨንቅ ነበር ከክፍሉ እንዳትገባ የተደረገችው ሳቤላ
ስለ በሽታው መባባስ ምንም አላወቀችም " ያን ያህል ሲያቃስት እንኳን ምንም ድምፅ ከጆሮዋ አልደረሰም » ስለዚህ ያለምንም ሐሳብና ጥርጣሬ እየሣቀችና
እየተጫወተች ደንገጡሯ ማርቨል እየረዳቻት መልበስ ጀመረች ማርቨል እመቤቷ የመረጠችውን ልብስና ጌጥ ሳትወደው እየከፋት አልብሳት አበቃች » ሳቤላ ልዩ ሁና
አጊጣና ለብሳ ወደ አባቷ ክፍል ገባች እንግዲህ ልሒድ አባባ ? » አለችው።
እሱም አዘብዝበው ያበጡትን ያይኑን ቆቦችና ደም የለበሰው ፊቱን ገለጥ አድርጎ” ሲያይ በትክክል ምን እንደምትመስል ባያረጋግጥም የምታምር ንግሥት የምታበራ መንፈስ መስላ ታየችው "ነጭ ዳንቴል ሥራ ቀሚስ ለብሳ አልማዟን በጸጉሯ ባንገቷና በክንዷ አድርጋለች " ቀሚሱ በጣም ምርጥ ከሆነ ጨርቅ የተስፋ ነበር " አልማዞቹ ከመልካሙ አንገቷና ከሚያሳሱት ክንዶቿ ላይ ሲብለጨለጩ ጫፉ
ቅልብስ ቅልብስ ብሎ የተበጠረ ከትከሻዋና ከደረቷ ወርዶ ከተኛው ጸጉሯ ጋር ልዩ ሁነው አምሮባት ነበር።
ኧርሉ ሲያያት በጣም ገረመውና ትክ ብሎ ካስተዋላት በኋላ «እንዴት ለአንድ የሙዚቃ ትርዒት እንደዚህ ሆነሽ ትለብሻለሽ ? አብደሽ ነው በጤናሽ ? » አላት
« ማርልም እንዳንተ አለችኝ » አለችው አሁንም በደስታ እየተፍነከነከች "
«እንዲያውም ልብሱንም አላቀርብም ብላኝ በግድ ነው ያስጣኋት እኔ ግን አባባ የሚስተር ኬንን ዝግጅት በደንብ ለብሰው ሊያዩት የሚገባ ትልቅ ትሮዒት
መሆኑን እነዚህ ዌስት ሊኖች እንዲያውቁት አስቤና ሆነ ብዬ ነው ያደረግሁት " »
« በአዳራሹ ያለው ሕዝብ በሙሉ እንደ ጉድ ይመለከትሻል »
« ግድ የለኝም " የፈለገ አፉን ከፍቶ ሲያየኝ ያምሽ ውጤቱን ይዠልህ እመጣለሁ " »
« ቀጣፊ በሰበቡ ለመታየት ፈልገሽ ነው እንጂ እንደዚህ የለበስሺው ግን ሳቤላ ...ኡ ኡኡ ! ኡህ ! ኡህ ! »
ሳቤላ እንደ ቆመች ድንግጥ አለች አባቷ ሲያቃስት ሰሚውን ያስጨንቅ ነበር
«ክፉ ልክፍት ! ልጄ . . . በይ ሒጂ ስናገር ይብስብኛል " »
« አባባ ልቅርና አጠገብህ ልሁንልህ ? » አለችው ኮስተር ብላ " ከማንኛውም ሐሳብና ሥራ በሽታ ይቀድማል " እንድቀር ከፈለግኸኝ ወይም የማደርግልህ ነገር
ቢኖር ልቅር " »
« እንዲያውም መሔድሺን እፈልገዋለሁ " ልታደርጊልኝ የምትችይው አንድም ምድራዊ ነገር ስለሌለ ሒጂ ይልቅስ ሚስተር ካርላይልን ያገኘሽው እንደሆነ ነገ ላነጋግረው እንደምፈልገው ንገሪው »
ማርቨል አንድ ካባ በትከሻዋ ላይ ጣል አዶረገችላትና ተዘጋጅቶ ሲጠብቅ ወደነበረው ሠረገላ ሔዳ ገባች።
የሙዚቃው ትርዒት ከገበያው ላይ ከነበረውና የከተማ አዳራሽ እየተባለ ከሚጠራው ከፍርድ ችሎት አዳራሽ ውስጥ ነበር " ድምፅ ለማስተጋባት የተመቸ
አዳራሽ ነበር ከዌስት ሊን የበለጡ በጣም የታወቁ ከተሞች እንኳን ይህን የሚያህል የሚመኩበት አዳራሽ አልነበራቸውም " ሚስተር ኬን ችሎታው በፈቀደለት መጠን ትርዒቱን ለማሳመር ሞከረ አንዲት በአራተኛ ደረጃ ልትመደብ
የምትችል ተጫወተች ከለንደን ቀጥሮ አምጥቶ ሌሎች አጃቢዎችም ከአካባቢው
አሟላ።
ባርባራ ሔርም የፈለገው ነገር ይምጣ እንጂ ትርዒቱን ሳታየው እንዶማትቀር አሳውቃ ነበር እናቷ ሚስዝ ሔር ግን ፍላጐቱም ጤንነቱም አልነበራትም" ስለዚህ
ሚስተር ሔርና ባርባራ ከሚስ እና ከሚስተር ካርላይል ጋር አብረው ለመሔድ ተነጋግረው ነበር ስለዚህ ቀደም ብለው በቡና ሰዓትላይ ለመድረስ ወደ ሚስ ካርላይል ቤት ሔዱ ከተገናኙ በኋላ በሠረገላ የመሔድ ነገር ሲነሣ ቦታው ቅርብ የምሽቱ
አየር ጥሩ ስለነበር ሚስ ካርላይል « እግሮቻችን ምን ሆኑና ነው ? » ብላ ተቃወመች " ባርባራም ከሚስተር ካርላይል ጋር እየተጫወተች በእግር መሔዱን አልጠላችውም " እነሆ ዳኛው ሔርና ሚስ ካርላይል ፊት ፊት እየተጫወቱ ሲሐዱ ባርባራና ሚስተር ካርላይል ቀረት ብለው እያወጉ ከኋላ ይከተሉ ነበር "
« እንዴት ነው አሁንስ ጠፋህሳ ? » አለችው ባርባራ "
«ሎርድ ዊልም ቬን ብቸኝነት እተሰማቸው ሲቸግሩ አየሁዋቸውና በየቀኑ ኢስት ሊን እተሻገርኩ አብሪአቸው ስለማመሽ ነው " ከእንግዲህ ግን ቅዳሜ ስለሚሔዱ በቂ ጊዜ ይኖረኛል።
« ትናንት ከደብሩ አለቃ ቤት ትመጣለህ ተብለህ ስትጠበቅ ነበር አኛም ማምሻውን ስንፈልግህ አመሸን»
« አለቃው ሚስተር ሊትልና ባለቤታቸው እንኳን የጠበቁኝ አልመሰለኝም ኢስት ሊን የራት ቀጠሮ እንደ ነበረኝ ነግሬአቸው ነበር »
« ኧረ ካልክስ አንዳንዶቹ ይህን ያህል ከዚያ ቤት የሚያመላልስህ ጉዳይ ምን እንደሆነ ይርማቸዋል " አጠቃሌለህ ኢስት ሊን ሳትግባ አትቀርም እየተባልክ ነው " እንዲያውም ሳቤላ ቬን እመቤት ሳቤላ ባትሆን ኖሮ ይህ ሁሉ ምልልስ እሷን ፍለጋ ነው ተብለህ ትታማ ነበር " »
ስለኔ ይህን ያህል በማሰባቸው አመሰግናለሁ የሚሰማኝ ደስታና የምቆጥርላቸው ውለታ እመቤት ሳቤላ ቬን ከሚሰማትና ከምትቈጥርላቸው የላቀ ሊሆን ይችላል " እኔን የገረመኝ ግን ባርባራ....አንቺም ይህን የማይረባ ወሬ ከቁም ነገር ቆጥረሽ ስትደግሚው ነው " »
« ሰው እኮ ነው እንዲህ የሚለው እኔ አላልኩ » አለችውና ነገሯን በመቀጠል! «ወይዘሮ ሳቤላ ድምፀ መልካም ናት የሚሏት እውነት ነው ? መቸም ያንጐራረች እንደሆነ የድምጿ ቃና ከሰማይ የወረደ እንጂ ከሰው አንደበት የወጣ አይመስልም አሉ።
« በይ ይህን አባባልሽን እኔ እንደ ሰማሁሽ ኮርሊያ እንዳትሰማሽ " ፊቷ የመልአክ ፊት ይመስላል » ስል ስምታኝ የቁጣ መዓት እንዳወረደችብኝ እንዳታወርድብሽ» አላት እየሣቀ።
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
...የሚስተር ኬን የሙዚቃ ትርዒት ሀሙስ ታይቶ ሲያበቃ ሎርድ ማውንት ስቨርን ቅዳሜውን ከኢስት ሊን ጓዙን ጠቅልሎ ለመነሳት አቀደ የጉዞው ዝግጅትም አስቀድሞ ተጀመረ ነግር ግን ቀኑ ከይረሰ በኋላ ያ ሁሉ የመነሳት ዝግጅት ለሁለተኛ ጊዜ እንዳይሰናከል አጠራጣሪ መስሎ ታየ ገና ሲነጋ ቤቱ ተሸበረ ከዌስትሊን ቀዶ ጠጋኝ ሐኪም ሚስተር ዌይን ራይት ተጠርቶሰ ከኧፕርሎ መኝታ ቤት
ገባ " ኧሮሎ አሁንም በሽታው እንደገና ክፉኛ ተቀሰቀሰበትና በጣም ተበሳጨ።
« በዚህ ዐይነት ገና ሳምንት ሁለት ሳምንት ወይም አንድ ወር እዚህ እቆይ ይሆናል » አላት ለሳቤላ ።
« በጣም አዝናለሁ... አባባ ኤስት ሊንን በጣም ስልችኸዋል " »
« መሰልቸት ይደለም ። ከኢስትሊን እንድወጣ የምፈልግበት ሌሎች ምክንያቶች አሉኝ አሁን ኮ አንቺም ወደ ሙዚቃ ትርዒት መሔድ ላትችይ ነው »
ሳቤላ ፊቷ ቀላ ። ምነው አባባ ? ላትችይ ነው አልከኝ?»
«አዎን ማን ይዞሽ ይሔዳል ? እኔ እንደ ሆንኩ ከመኝታዬ እንኳን መነሣት አልቻልኩም »
« መገኘት አለብኝ . . . አባባ " አለዚያማ እንግኛለን ብለን አስወርተን ብንቀር ዱሮውንም እንደማናደርገው አወቀን ያስወራነው ይመስልብናል " ደግሞ እንደምታውቀው ከዱሲ ቤተሰብ ጋር እዚያ ለመናኘት †ቃጥረናል " ባይሆን ሠረገላው እዚያው ያድርሰኝና እኔ ከነሱ ጋር እገባለሁ" »
« በይ እሺ ላንቺ ደስ እንዲለሽ እኔ እንኳን የምትቀሪበትን ስበብ ካገኘሽ እንዳጋጣ ቀርተሽ የምትጠቀሚበት መስሎኝ ነበር » አላት "
« በጭራሽ ! እኔ ሚስተር ኬንን ከነሙዚቃው የማልንቀው መሆኔን ዌስት ሊን እንዲያይ እፈልጋለሁ » አለች ሳቤላ እየሣቀች ።
ቀን ላይ የዊልያም ቬን በሽታ በጣም ከሚያሳስብ ደረጃ ላይ ደረሰ " ስቃዩ በጣም የሚያሰቅቅና የሚያስጨንቅ ነበር ከክፍሉ እንዳትገባ የተደረገችው ሳቤላ
ስለ በሽታው መባባስ ምንም አላወቀችም " ያን ያህል ሲያቃስት እንኳን ምንም ድምፅ ከጆሮዋ አልደረሰም » ስለዚህ ያለምንም ሐሳብና ጥርጣሬ እየሣቀችና
እየተጫወተች ደንገጡሯ ማርቨል እየረዳቻት መልበስ ጀመረች ማርቨል እመቤቷ የመረጠችውን ልብስና ጌጥ ሳትወደው እየከፋት አልብሳት አበቃች » ሳቤላ ልዩ ሁና
አጊጣና ለብሳ ወደ አባቷ ክፍል ገባች እንግዲህ ልሒድ አባባ ? » አለችው።
እሱም አዘብዝበው ያበጡትን ያይኑን ቆቦችና ደም የለበሰው ፊቱን ገለጥ አድርጎ” ሲያይ በትክክል ምን እንደምትመስል ባያረጋግጥም የምታምር ንግሥት የምታበራ መንፈስ መስላ ታየችው "ነጭ ዳንቴል ሥራ ቀሚስ ለብሳ አልማዟን በጸጉሯ ባንገቷና በክንዷ አድርጋለች " ቀሚሱ በጣም ምርጥ ከሆነ ጨርቅ የተስፋ ነበር " አልማዞቹ ከመልካሙ አንገቷና ከሚያሳሱት ክንዶቿ ላይ ሲብለጨለጩ ጫፉ
ቅልብስ ቅልብስ ብሎ የተበጠረ ከትከሻዋና ከደረቷ ወርዶ ከተኛው ጸጉሯ ጋር ልዩ ሁነው አምሮባት ነበር።
ኧርሉ ሲያያት በጣም ገረመውና ትክ ብሎ ካስተዋላት በኋላ «እንዴት ለአንድ የሙዚቃ ትርዒት እንደዚህ ሆነሽ ትለብሻለሽ ? አብደሽ ነው በጤናሽ ? » አላት
« ማርልም እንዳንተ አለችኝ » አለችው አሁንም በደስታ እየተፍነከነከች "
«እንዲያውም ልብሱንም አላቀርብም ብላኝ በግድ ነው ያስጣኋት እኔ ግን አባባ የሚስተር ኬንን ዝግጅት በደንብ ለብሰው ሊያዩት የሚገባ ትልቅ ትሮዒት
መሆኑን እነዚህ ዌስት ሊኖች እንዲያውቁት አስቤና ሆነ ብዬ ነው ያደረግሁት " »
« በአዳራሹ ያለው ሕዝብ በሙሉ እንደ ጉድ ይመለከትሻል »
« ግድ የለኝም " የፈለገ አፉን ከፍቶ ሲያየኝ ያምሽ ውጤቱን ይዠልህ እመጣለሁ " »
« ቀጣፊ በሰበቡ ለመታየት ፈልገሽ ነው እንጂ እንደዚህ የለበስሺው ግን ሳቤላ ...ኡ ኡኡ ! ኡህ ! ኡህ ! »
ሳቤላ እንደ ቆመች ድንግጥ አለች አባቷ ሲያቃስት ሰሚውን ያስጨንቅ ነበር
«ክፉ ልክፍት ! ልጄ . . . በይ ሒጂ ስናገር ይብስብኛል " »
« አባባ ልቅርና አጠገብህ ልሁንልህ ? » አለችው ኮስተር ብላ " ከማንኛውም ሐሳብና ሥራ በሽታ ይቀድማል " እንድቀር ከፈለግኸኝ ወይም የማደርግልህ ነገር
ቢኖር ልቅር " »
« እንዲያውም መሔድሺን እፈልገዋለሁ " ልታደርጊልኝ የምትችይው አንድም ምድራዊ ነገር ስለሌለ ሒጂ ይልቅስ ሚስተር ካርላይልን ያገኘሽው እንደሆነ ነገ ላነጋግረው እንደምፈልገው ንገሪው »
ማርቨል አንድ ካባ በትከሻዋ ላይ ጣል አዶረገችላትና ተዘጋጅቶ ሲጠብቅ ወደነበረው ሠረገላ ሔዳ ገባች።
የሙዚቃው ትርዒት ከገበያው ላይ ከነበረውና የከተማ አዳራሽ እየተባለ ከሚጠራው ከፍርድ ችሎት አዳራሽ ውስጥ ነበር " ድምፅ ለማስተጋባት የተመቸ
አዳራሽ ነበር ከዌስት ሊን የበለጡ በጣም የታወቁ ከተሞች እንኳን ይህን የሚያህል የሚመኩበት አዳራሽ አልነበራቸውም " ሚስተር ኬን ችሎታው በፈቀደለት መጠን ትርዒቱን ለማሳመር ሞከረ አንዲት በአራተኛ ደረጃ ልትመደብ
የምትችል ተጫወተች ከለንደን ቀጥሮ አምጥቶ ሌሎች አጃቢዎችም ከአካባቢው
አሟላ።
ባርባራ ሔርም የፈለገው ነገር ይምጣ እንጂ ትርዒቱን ሳታየው እንዶማትቀር አሳውቃ ነበር እናቷ ሚስዝ ሔር ግን ፍላጐቱም ጤንነቱም አልነበራትም" ስለዚህ
ሚስተር ሔርና ባርባራ ከሚስ እና ከሚስተር ካርላይል ጋር አብረው ለመሔድ ተነጋግረው ነበር ስለዚህ ቀደም ብለው በቡና ሰዓትላይ ለመድረስ ወደ ሚስ ካርላይል ቤት ሔዱ ከተገናኙ በኋላ በሠረገላ የመሔድ ነገር ሲነሣ ቦታው ቅርብ የምሽቱ
አየር ጥሩ ስለነበር ሚስ ካርላይል « እግሮቻችን ምን ሆኑና ነው ? » ብላ ተቃወመች " ባርባራም ከሚስተር ካርላይል ጋር እየተጫወተች በእግር መሔዱን አልጠላችውም " እነሆ ዳኛው ሔርና ሚስ ካርላይል ፊት ፊት እየተጫወቱ ሲሐዱ ባርባራና ሚስተር ካርላይል ቀረት ብለው እያወጉ ከኋላ ይከተሉ ነበር "
« እንዴት ነው አሁንስ ጠፋህሳ ? » አለችው ባርባራ "
«ሎርድ ዊልም ቬን ብቸኝነት እተሰማቸው ሲቸግሩ አየሁዋቸውና በየቀኑ ኢስት ሊን እተሻገርኩ አብሪአቸው ስለማመሽ ነው " ከእንግዲህ ግን ቅዳሜ ስለሚሔዱ በቂ ጊዜ ይኖረኛል።
« ትናንት ከደብሩ አለቃ ቤት ትመጣለህ ተብለህ ስትጠበቅ ነበር አኛም ማምሻውን ስንፈልግህ አመሸን»
« አለቃው ሚስተር ሊትልና ባለቤታቸው እንኳን የጠበቁኝ አልመሰለኝም ኢስት ሊን የራት ቀጠሮ እንደ ነበረኝ ነግሬአቸው ነበር »
« ኧረ ካልክስ አንዳንዶቹ ይህን ያህል ከዚያ ቤት የሚያመላልስህ ጉዳይ ምን እንደሆነ ይርማቸዋል " አጠቃሌለህ ኢስት ሊን ሳትግባ አትቀርም እየተባልክ ነው " እንዲያውም ሳቤላ ቬን እመቤት ሳቤላ ባትሆን ኖሮ ይህ ሁሉ ምልልስ እሷን ፍለጋ ነው ተብለህ ትታማ ነበር " »
ስለኔ ይህን ያህል በማሰባቸው አመሰግናለሁ የሚሰማኝ ደስታና የምቆጥርላቸው ውለታ እመቤት ሳቤላ ቬን ከሚሰማትና ከምትቈጥርላቸው የላቀ ሊሆን ይችላል " እኔን የገረመኝ ግን ባርባራ....አንቺም ይህን የማይረባ ወሬ ከቁም ነገር ቆጥረሽ ስትደግሚው ነው " »
« ሰው እኮ ነው እንዲህ የሚለው እኔ አላልኩ » አለችውና ነገሯን በመቀጠል! «ወይዘሮ ሳቤላ ድምፀ መልካም ናት የሚሏት እውነት ነው ? መቸም ያንጐራረች እንደሆነ የድምጿ ቃና ከሰማይ የወረደ እንጂ ከሰው አንደበት የወጣ አይመስልም አሉ።
« በይ ይህን አባባልሽን እኔ እንደ ሰማሁሽ ኮርሊያ እንዳትሰማሽ " ፊቷ የመልአክ ፊት ይመስላል » ስል ስምታኝ የቁጣ መዓት እንዳወረደችብኝ እንዳታወርድብሽ» አላት እየሣቀ።
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የእናታችን ታሪክ
ከአያታችን መሄድ በኋላ ከማዘንና ከመበሳጨት ውጪ ምን ማድረግ ወይም ምን ማለት ወይም ምን ሊሰማን እንደሚገባ አልገባንም እናታችን ሹራቧን መልሳ ስትለብስ ስመለከታት ልቤ በውስጤ ተርገበገበ፡ ሹራቧን ቀሚሷ
ውስጥ እየወሸቀች ወደ እኛ ዞራ ደህና እንደሚሆን ለማረጋገጫ ለሁላችንም ደስ የሚል ፈገግታ አሳየችን እንደዚያ ካለው ፈገግታ ውስጥ የሆነ ነገር መጨበጥ አለመቻሌ ያሳዝናል፡ ክሪስ አይኖቹን ወለሉ ላይ ተክሎ የተነጠፈው አሮጌ ምንጣፍ ላይ ያሉትን ዲዛይኖች በጫማው በመከተል ገና ያልተረጋጋ
ቁጣውን እየገለፀ ነው።
“አሁን ተመልከቱ አለች እናታችን በውሸት ደስታ። “ብዙምኮ አያምም። ከስጋዬ ይልቅ የተሰቃየው ክብሬ ነው እንደ ባሪያ ወይም እንደ እንስሳ መገረፍ በጣም የሚያሳፍር ነገር ነው በተለይ ደግሞ በራስህ ወላጆች።
ግን እንደዚህ አይነት ግርፊያ እንደገና ይኖራል ብላችሁ አትጨነቁ። በቃ አንድ ጊዜ ብቻ ነው: ከአባታችሁና ከእናንተ ጋር የኖርኳቸውን አይነት በደስታ የተሞሉ ተጨማሪ አስራ አምስት አመታት ለመኖር ብችል የዚህን
ግርፊያ መቶ እጥፍ እንኳን እቋቋማለሁ ነፍሴን ቢያሸማቅቃትም ያደረጉኝን
እንዳሳያችሁ አደረጉኝ...” አልጋ ላይ ተቀመጠችና ተጠግተን እንድናቅፋት እጆቿን ዘረጋችልን ሁላችንም ወደሷ ሄደን ተጠመጠምንባት እኔ ግን
ሳቅፋት እንዳላሳምማት እየተጠነቀቅኩ ነበር። መንትዮቹን ብድግ አድርጋ ጭኖቿ ላይ አስቀመጠችና ለእኛ አልጋውን መታ መታ እያደረገች አልጋው
ላይ እንድንቀመጥ ነገረችን፡ ከዚያ መናገር ጀመረች: ልትናገር የፈለገችው ነገር ለእሷ ከባድ ቢሆንም፣ እኛም ለመስማት የዚያኑ ያህል ከባድ ሆኖብን
ነበር።
“በጥንቃቄ እንድታዳምጡኝና አሁን የምነግራችሁን ነገሮች እድሜያችሁን ሙሉ እንድታስታውሷቸው እፈልጋለሁ" መናገሯን ቆም አድርጋ ግድግዳዎቹ ወደ ውጪ ያሳዩ ይመስል እና በእነሱ ውስጥ የዚህን ግዙፍ ቤት ሌሎች
ክፍሎች የምታይ ይመስል ግድግዳው ላይ አፍጥጣ ቆየችና “ይሄ እንግዳ የሆነ ቤት ነው: በውስጡ የሚኖሩት ሰዎች ግን፣ እንግዶችም ሠራተኞችም
ሳይሆኑ ወላጆቼ ናቸው- አያቶቻችሁ አክራሪ ሀይማኖተኞች ስለመሆናቸው ላስጠነቅቃችሁ ይገባ ነበር በእግዚአብሔር ማመን ጥሩና ትክክል ነገር ነው፡ ነገር ግን እምነታችሁን ከብሉይ ኪዳን ላይ የምትፈልጓቸውን ቃላት
ብቻ በመውሰድ የምታጠነክሩ ከሆነና የእናንተን ፍላጎት በሚያሟላ መንገድ የምትተረጉሙት ከሆነ፣ ያ ግብዝነት ነው፡ እና ወላጆቼም ልክ እንደዚያ ናቸው።
“አባቴ እየሞተ ነው፡ ነገር ግን ሁልጊዜ እሁድ እሁድ ተሸክመው ወደ ቤተክርስቲያን ይወስዱታል ሻል ካለው በዊልቸር ላይ፣ ከባሰበት ደግሞ ቃሬዛ ላይ አጋድመው ይወስዱትና የሚፈለግበትን አስር በመቶ አስራቱን ከአመት ገቢው ላይ ይሰጣል።
“ቤተክርስቲያኗን ለማሰራት ገንዘብ ሰጥቷል፤ መስኮቶችን ሁሉ ያስገጠመው ራሱ ነው: ቤተክርስቲያኗንና አገልግሎቱን ሁሉ ተቆጣጥሯል። በዚህም
የመንግስተ ሰማያት መንገዱ በወርቅ ላይ እንደሚሆን አረጋግጧል አባቴ በእርግጠኝነት ለቅዱስ ጴጥሮስ ጉቦ በመስጠት መንግስተ ሰማያት መግባት
እንደሚችል ያስባል። በዚያ ቤተክርስቲያን እሱ ራሱ እንደ አምላክ ወይም እንደ ቅዱስ ይታያል እናም ከቤተክርስትያን መልስ ወደ ቤቱ ሲመጣ፣
የሚፈልገውን ለማድረግ ሙሉ በሙሉ ፈቃድ እንዳለው ያስባል ምክንያቱም እዚያ የሚጠበቅበትን ሰርቶ ጨርሷል፡ በራሱ መንገድ ከፍሏል፤ ስለዚህ ከገሀነም ድኗል።
“ከሁለት ታላላቅ ወንድሞቼ ጋር ስናድግ ቤተክርስቲያን እንድንሄድ እንገደድ ነበር፡ ከአልጋ የማያስነሳ በሽታ ቢያመንም እንኳን መሄድ ነበረብን ኃይማኖት ኑሯችንን አንቆ ይዞት ነበር። መልካም ሁኑ፣ መልካም ሁኑ፣ መልካም ሁኑ፣ ሁልጊዜ የምንሰማው ይህንን ነበር ሁልጊዜም ሌሎች ሰዎች
አድርገውት የሚደሰቱበት ነገር ሁሉ እኛ ጋ ሲደርስ ኃጢአት ይሆናል። ወንድሞቼና እኔ ዋና መሄድ አይፈቀድልንም ነበር ምክንያቱ ደግሞ ዋና
መዋኘት ማለት የዋና ልብስ በመልበስ አብዛኛውን የሰውነታችንን ክፍል ለእይታ ማጋለጥ ስለሆነ ነበር። ካርታ መጫወትም ሆነ ሌሎች ቁማርን
የሚያመለክቱ ጨዋታዎችን መጫወት የተከለከለ ነበር: ወደ ዳንስ ቦታዎች መሄድ አይፈቅድልንም:: ምክንያቱ ደግሞ ምናልባት ሰውነታችን ከተቃራኒ ፆታ ሰውነት ጋር ሊነካካ ስለሚችል ሀሳቦቻችንን እንድንቆጣጠርና ስለተቃራኒ ፆታ ግንኙነት እንዳናስብ መጠንቀቅ ነበረብን፡ የኃጢአት ሀሳቦች እንደ ድርጊቶቹ
ሁሉ ክፉ ናቸው እንባል ነበር እንዳናደርጋቸው ስለምንከላከላቸው ነገሮች
ብዙ መቀጠል እችላለሁ በአጠቃላይ አስደሳችና አስገራሚ የሆኑ ነገሮች ሁሉ ለእነርሱ ኃጢአት ይመስሉ ነበር ህይወት በጣም ስርዓት የበዛበት ሲሆን
ልጆች የተከለከሉትን ነገሮች ለማድረግ የበለጠ ፍላጎት እንዲያድርባቸውና እንዲያምፁ የሚያደርጋቸው የሆነ ነገር አለ ወላጆቻችን ሶስቱን ልጆቻቸውን
እንደ መልአክትና ቅዱሳን አድርገው ለማሳደግ ቢፈልጉም፣ የተሳካላቸው መጥፎ ሆነን እንድናድግ ማድረግ ብቻ ነው::"
አይኖቼ ፈጠው አፌ እንደተለጎመ ተቀመጥኩ፡ ሁላችንም እንደዚያ ሆነን ነበር መንትዮቹ ሳይቀር: “ከዚያ አንድ ቀን…” እናታችን ቀጠለች በዚህ ሁሉ መሀከል አንድ ቆንጆ ወጣት ከእኛ ጋር ሊኖር መጣ፡ አባቱ አያቴ ነበር። የሞተውም ይህ ወጣት ገና የሶስት ዓመት ልጅ ሳለ ነበር። የእናቱ ስም አሊሺያ ሲሆን፣ የአምሳ አምስት አመት ዕድሜ የነበረውን አያቴን ስታገባ ገና
አስራ ስድስት አመቷ ነበር፡ አሊሽያ በልጅነቷ ነው የሞተችው: የአያቴ ስም ጋርላንድ ክሪስቶፈር ፎክስወርዝ ነበር፡ እና እሱ ሲሞት ግማሽ ሀብቱ የሶስት አመት እድሜ ወደ ነበረው ወደ ትንሹ ልጅ ሄደ ነገር ግን አባቴ ማልኮልም ራሱን በሞግዚትነት ሰይሞ የአባትየውን ንብረት ሁሉ መቆጣጠር ቻለ።በእርግጥም የሶስት አመት ህፃን በጉዳዩ ላይ ድምፅ አልነበረውም እናቱም
እንድትደግፍ አልተደረገችም:
“አባቴ አንድ ጊዜ ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር ካደረገ በኋላ አሊሺያንና ትንሹን ልጅ አስወጥቶ አባረራቸው: የአሊሺያ ወላጆች ወደሚኖሩበት ሪችመንድ ሄዱና
ለሁለተኛ ጊዜ እስክታገባ ድረስ እዚያ ተቀመጡ። ከልጅነቷ ጀምሮ ትወደው ከነበረ ሰው ጋር ለተወሰነ አመት በደስታ ኖረችና እሱም ሞተ። ሁለት ጊዜ አገባች ሁለት ጊዜም ባሎቿ ሞቱባት አሁን ወላጆቿም ሞተው ስለነበር
ከትንሹ ልጇ ጋር ብቻዋን ቀረች: ከጥቂት ዓመታት በኋላ እሷም በካንሰር ሞተች፡ የዚያን ጊዜ ነው ልጇ ጋርላንድ ክሪስቶፈር ፎክስርወርዝ አራተኛ እዚህ ሊኖር የመጣው: ክሪስ ብለን ነበር የምንጠራው…” አመነታች ከዚያ
ክሪስና እኔን በክንዶቿ ጠበቅ አደረገችን፡ “…ስለማን እያወራሁ እንደሆነ አውቃችኋል? ያ ወጣት ልጅ ማን እንደሆነ ገመታችሁ?”
ተንቀጠቀጥኩ ሚስጥራዊው አጎት እና በሹክሹክታ “አባዬ የምታወሪው ስለ አባዬ ነው:” አልኩ
“አዎ” አለች። ከዚያ በከባዱ ተነፈሰች።
ትልቅ ወንድሜን ለማየት ወደፊት ሳብ አልኩ። አይኖቹ መስታወት መስለው ፊቱ ላይ መገረም እየተነበበ በፀጥታ ተቀምጧል።
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
የእናታችን ታሪክ
ከአያታችን መሄድ በኋላ ከማዘንና ከመበሳጨት ውጪ ምን ማድረግ ወይም ምን ማለት ወይም ምን ሊሰማን እንደሚገባ አልገባንም እናታችን ሹራቧን መልሳ ስትለብስ ስመለከታት ልቤ በውስጤ ተርገበገበ፡ ሹራቧን ቀሚሷ
ውስጥ እየወሸቀች ወደ እኛ ዞራ ደህና እንደሚሆን ለማረጋገጫ ለሁላችንም ደስ የሚል ፈገግታ አሳየችን እንደዚያ ካለው ፈገግታ ውስጥ የሆነ ነገር መጨበጥ አለመቻሌ ያሳዝናል፡ ክሪስ አይኖቹን ወለሉ ላይ ተክሎ የተነጠፈው አሮጌ ምንጣፍ ላይ ያሉትን ዲዛይኖች በጫማው በመከተል ገና ያልተረጋጋ
ቁጣውን እየገለፀ ነው።
“አሁን ተመልከቱ አለች እናታችን በውሸት ደስታ። “ብዙምኮ አያምም። ከስጋዬ ይልቅ የተሰቃየው ክብሬ ነው እንደ ባሪያ ወይም እንደ እንስሳ መገረፍ በጣም የሚያሳፍር ነገር ነው በተለይ ደግሞ በራስህ ወላጆች።
ግን እንደዚህ አይነት ግርፊያ እንደገና ይኖራል ብላችሁ አትጨነቁ። በቃ አንድ ጊዜ ብቻ ነው: ከአባታችሁና ከእናንተ ጋር የኖርኳቸውን አይነት በደስታ የተሞሉ ተጨማሪ አስራ አምስት አመታት ለመኖር ብችል የዚህን
ግርፊያ መቶ እጥፍ እንኳን እቋቋማለሁ ነፍሴን ቢያሸማቅቃትም ያደረጉኝን
እንዳሳያችሁ አደረጉኝ...” አልጋ ላይ ተቀመጠችና ተጠግተን እንድናቅፋት እጆቿን ዘረጋችልን ሁላችንም ወደሷ ሄደን ተጠመጠምንባት እኔ ግን
ሳቅፋት እንዳላሳምማት እየተጠነቀቅኩ ነበር። መንትዮቹን ብድግ አድርጋ ጭኖቿ ላይ አስቀመጠችና ለእኛ አልጋውን መታ መታ እያደረገች አልጋው
ላይ እንድንቀመጥ ነገረችን፡ ከዚያ መናገር ጀመረች: ልትናገር የፈለገችው ነገር ለእሷ ከባድ ቢሆንም፣ እኛም ለመስማት የዚያኑ ያህል ከባድ ሆኖብን
ነበር።
“በጥንቃቄ እንድታዳምጡኝና አሁን የምነግራችሁን ነገሮች እድሜያችሁን ሙሉ እንድታስታውሷቸው እፈልጋለሁ" መናገሯን ቆም አድርጋ ግድግዳዎቹ ወደ ውጪ ያሳዩ ይመስል እና በእነሱ ውስጥ የዚህን ግዙፍ ቤት ሌሎች
ክፍሎች የምታይ ይመስል ግድግዳው ላይ አፍጥጣ ቆየችና “ይሄ እንግዳ የሆነ ቤት ነው: በውስጡ የሚኖሩት ሰዎች ግን፣ እንግዶችም ሠራተኞችም
ሳይሆኑ ወላጆቼ ናቸው- አያቶቻችሁ አክራሪ ሀይማኖተኞች ስለመሆናቸው ላስጠነቅቃችሁ ይገባ ነበር በእግዚአብሔር ማመን ጥሩና ትክክል ነገር ነው፡ ነገር ግን እምነታችሁን ከብሉይ ኪዳን ላይ የምትፈልጓቸውን ቃላት
ብቻ በመውሰድ የምታጠነክሩ ከሆነና የእናንተን ፍላጎት በሚያሟላ መንገድ የምትተረጉሙት ከሆነ፣ ያ ግብዝነት ነው፡ እና ወላጆቼም ልክ እንደዚያ ናቸው።
“አባቴ እየሞተ ነው፡ ነገር ግን ሁልጊዜ እሁድ እሁድ ተሸክመው ወደ ቤተክርስቲያን ይወስዱታል ሻል ካለው በዊልቸር ላይ፣ ከባሰበት ደግሞ ቃሬዛ ላይ አጋድመው ይወስዱትና የሚፈለግበትን አስር በመቶ አስራቱን ከአመት ገቢው ላይ ይሰጣል።
“ቤተክርስቲያኗን ለማሰራት ገንዘብ ሰጥቷል፤ መስኮቶችን ሁሉ ያስገጠመው ራሱ ነው: ቤተክርስቲያኗንና አገልግሎቱን ሁሉ ተቆጣጥሯል። በዚህም
የመንግስተ ሰማያት መንገዱ በወርቅ ላይ እንደሚሆን አረጋግጧል አባቴ በእርግጠኝነት ለቅዱስ ጴጥሮስ ጉቦ በመስጠት መንግስተ ሰማያት መግባት
እንደሚችል ያስባል። በዚያ ቤተክርስቲያን እሱ ራሱ እንደ አምላክ ወይም እንደ ቅዱስ ይታያል እናም ከቤተክርስትያን መልስ ወደ ቤቱ ሲመጣ፣
የሚፈልገውን ለማድረግ ሙሉ በሙሉ ፈቃድ እንዳለው ያስባል ምክንያቱም እዚያ የሚጠበቅበትን ሰርቶ ጨርሷል፡ በራሱ መንገድ ከፍሏል፤ ስለዚህ ከገሀነም ድኗል።
“ከሁለት ታላላቅ ወንድሞቼ ጋር ስናድግ ቤተክርስቲያን እንድንሄድ እንገደድ ነበር፡ ከአልጋ የማያስነሳ በሽታ ቢያመንም እንኳን መሄድ ነበረብን ኃይማኖት ኑሯችንን አንቆ ይዞት ነበር። መልካም ሁኑ፣ መልካም ሁኑ፣ መልካም ሁኑ፣ ሁልጊዜ የምንሰማው ይህንን ነበር ሁልጊዜም ሌሎች ሰዎች
አድርገውት የሚደሰቱበት ነገር ሁሉ እኛ ጋ ሲደርስ ኃጢአት ይሆናል። ወንድሞቼና እኔ ዋና መሄድ አይፈቀድልንም ነበር ምክንያቱ ደግሞ ዋና
መዋኘት ማለት የዋና ልብስ በመልበስ አብዛኛውን የሰውነታችንን ክፍል ለእይታ ማጋለጥ ስለሆነ ነበር። ካርታ መጫወትም ሆነ ሌሎች ቁማርን
የሚያመለክቱ ጨዋታዎችን መጫወት የተከለከለ ነበር: ወደ ዳንስ ቦታዎች መሄድ አይፈቅድልንም:: ምክንያቱ ደግሞ ምናልባት ሰውነታችን ከተቃራኒ ፆታ ሰውነት ጋር ሊነካካ ስለሚችል ሀሳቦቻችንን እንድንቆጣጠርና ስለተቃራኒ ፆታ ግንኙነት እንዳናስብ መጠንቀቅ ነበረብን፡ የኃጢአት ሀሳቦች እንደ ድርጊቶቹ
ሁሉ ክፉ ናቸው እንባል ነበር እንዳናደርጋቸው ስለምንከላከላቸው ነገሮች
ብዙ መቀጠል እችላለሁ በአጠቃላይ አስደሳችና አስገራሚ የሆኑ ነገሮች ሁሉ ለእነርሱ ኃጢአት ይመስሉ ነበር ህይወት በጣም ስርዓት የበዛበት ሲሆን
ልጆች የተከለከሉትን ነገሮች ለማድረግ የበለጠ ፍላጎት እንዲያድርባቸውና እንዲያምፁ የሚያደርጋቸው የሆነ ነገር አለ ወላጆቻችን ሶስቱን ልጆቻቸውን
እንደ መልአክትና ቅዱሳን አድርገው ለማሳደግ ቢፈልጉም፣ የተሳካላቸው መጥፎ ሆነን እንድናድግ ማድረግ ብቻ ነው::"
አይኖቼ ፈጠው አፌ እንደተለጎመ ተቀመጥኩ፡ ሁላችንም እንደዚያ ሆነን ነበር መንትዮቹ ሳይቀር: “ከዚያ አንድ ቀን…” እናታችን ቀጠለች በዚህ ሁሉ መሀከል አንድ ቆንጆ ወጣት ከእኛ ጋር ሊኖር መጣ፡ አባቱ አያቴ ነበር። የሞተውም ይህ ወጣት ገና የሶስት ዓመት ልጅ ሳለ ነበር። የእናቱ ስም አሊሺያ ሲሆን፣ የአምሳ አምስት አመት ዕድሜ የነበረውን አያቴን ስታገባ ገና
አስራ ስድስት አመቷ ነበር፡ አሊሽያ በልጅነቷ ነው የሞተችው: የአያቴ ስም ጋርላንድ ክሪስቶፈር ፎክስወርዝ ነበር፡ እና እሱ ሲሞት ግማሽ ሀብቱ የሶስት አመት እድሜ ወደ ነበረው ወደ ትንሹ ልጅ ሄደ ነገር ግን አባቴ ማልኮልም ራሱን በሞግዚትነት ሰይሞ የአባትየውን ንብረት ሁሉ መቆጣጠር ቻለ።በእርግጥም የሶስት አመት ህፃን በጉዳዩ ላይ ድምፅ አልነበረውም እናቱም
እንድትደግፍ አልተደረገችም:
“አባቴ አንድ ጊዜ ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር ካደረገ በኋላ አሊሺያንና ትንሹን ልጅ አስወጥቶ አባረራቸው: የአሊሺያ ወላጆች ወደሚኖሩበት ሪችመንድ ሄዱና
ለሁለተኛ ጊዜ እስክታገባ ድረስ እዚያ ተቀመጡ። ከልጅነቷ ጀምሮ ትወደው ከነበረ ሰው ጋር ለተወሰነ አመት በደስታ ኖረችና እሱም ሞተ። ሁለት ጊዜ አገባች ሁለት ጊዜም ባሎቿ ሞቱባት አሁን ወላጆቿም ሞተው ስለነበር
ከትንሹ ልጇ ጋር ብቻዋን ቀረች: ከጥቂት ዓመታት በኋላ እሷም በካንሰር ሞተች፡ የዚያን ጊዜ ነው ልጇ ጋርላንድ ክሪስቶፈር ፎክስርወርዝ አራተኛ እዚህ ሊኖር የመጣው: ክሪስ ብለን ነበር የምንጠራው…” አመነታች ከዚያ
ክሪስና እኔን በክንዶቿ ጠበቅ አደረገችን፡ “…ስለማን እያወራሁ እንደሆነ አውቃችኋል? ያ ወጣት ልጅ ማን እንደሆነ ገመታችሁ?”
ተንቀጠቀጥኩ ሚስጥራዊው አጎት እና በሹክሹክታ “አባዬ የምታወሪው ስለ አባዬ ነው:” አልኩ
“አዎ” አለች። ከዚያ በከባዱ ተነፈሰች።
ትልቅ ወንድሜን ለማየት ወደፊት ሳብ አልኩ። አይኖቹ መስታወት መስለው ፊቱ ላይ መገረም እየተነበበ በፀጥታ ተቀምጧል።
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ማርክ አልደር በመጀመሪያ ዳያና ላቭሴይንን ያያት ጊዜ ‹‹የአምላክ ያለህ! እንዳንቺ የምታምር ሴት አይቼ አላውቅም›› አላት፡፡
ያገኛት ሁሉ እንዲህ ይላታል፡፡ ዲያና ያለጥርጥር ውብ ሴት ስትሆን ጥሩ ጥሩ ልብስ መልበስም ትወዳለች፡፡ የዚያን ቀን እጀ ጉርድ ቅልጥሟ ጋ የሚደርስ ቀሚስ ለብሳ ነበር፡፡ እንዳማረባትም አውቃለች።
ማንቼስተር ከተማ ሚድላንድ ሆቴል ውስጥ ራት ግብዣ ተጠርታለች
በግብዣው ላይ ከነበሩት ከባሏ የንግድ ሸሪኮች ጋር በሙሉ ስትደንስ አመሸች ታዲያ ሁሉም አብረዋት የደነሱት ወንዶች ደረታቸው ላይ ይለጥፏታል ወይም እግሯ ላይ ይቆማሉ ሚስቶቻቸው ደግሞ በጥላቻ ዐይን አፈር ድሜ ያስግጧታል፡ ወንዶች ቆንጆ ሴት አይተው ሲቅበጠበጡ
ሚስቶች ለምን ባሎቻቸውን ትተው ሴቷ ላይ በቁጣ እንደሚያፈጡ ሁልጊዜ
ይገርማታል፡፡ እሷ እንደሆነ እነዚህን ጉረኛና በዊስኪ የደነበዙ ባሎቻቸውን
አትፈልግም፡፡
አንድ ጊዜማ የከተማውን ምክትል ከንቲባ በሰው ፊት በማዋረዷ ባሏን አሳፍራው ነበር፡ በኋላም ትንሽ እረፍት አገኝ ብላ ሲጋራ የምትገዛ መስላ ከሆቴሉ ወጥታ ሄደች፡
ኮኛኩን እየተጎነጨ ብቻውን ተቀምጧል። ልክ በክፍሉ ውስጥ የፀሃይ ብርሃን የፈነጠቀች ይመስል ስትገባ ዓይኑን ተከለባት፡ ሰውዬው አጠር ያለና እንደ ህፃን ፍልቅልቅ ያለ ፈገግታ የተላበሰ ሲሆን አሜሪካዊ መሆኑ ሁኔታው ያሳብቅበታል፡፡ ገና እንዳያት አድናቆቱን የገለፀላት ሲሆን ሰውዬው የደስ ደስ ያለው በመሆኑ ፈገግ ብትልለትም አላናገረችውም፡፡ ሲጋራዋን
ገዝታ ቀዝቃዛ ውሃ በጉሮሮዋ ለቀቀችና ወደ ዳንሱ አዳራሽ ተመለሰች፡
ሰውዬው ማን እንደሆነች ከቡና ቤቱ አስተናጋጅ ጠየቀና አድራሻዋን
እንደምንም አግኝቶ የፍቅር ግጥም ፅፎ ላከላት፡፡ ግጥሙን ስታነብ አነባች፡፡
ያስለቀሳት ብዙ ነገር ተመኝታ ሁሉንም ነገር ባለማግኘቷ ነው፡፡ ያለቀሰችው በዚች ደስታ በራቃት ከተማ የዓመት እረፍት መውጣት ከሚጠላ ባሏ ጋር ተጣብቃ በመቅረቷ ነው፡፡ ያለቀሰችው ከአምስት ዓመት ወዲህ ለመጀመሪያ
ጊዜ የፍቅር ግጥም በመስማቷ ነው: ያለቀሰችው ለመርቪን ያላት ፍቅር የተሟጠጠ በመሆኑ ነው፡፡
በነጋታው እሁድ ስለነበር ዳያና ቤቷ ውስጥ መሸገች፡፡ ሰኞ ዕለት ወደ
ከተማው መጽሐፍ ቤት ሄዳ ከዚህ ቀደም የተዋሰችውን መጽሐፍ መለሰችና ፊልም ቤት ገባች፡፡ ከዚያም ለእህቷ ልጆች ስጦታ ስትገዛ ዋለች፡፡ በኋላም
እራት መስሪያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ገዛችና ከከተማ ወጣ ወዳለው መኖሪያዋ
በጊዜ ለመድረስ ባቡር ላይ ተሳፈረች፡፡ ከተማ ውስጥ ስትዟዟርና ቡና ስትጠጣ የአሜሪካዊ አነጋገር ቅላፄ ያለውን ሰው ሳታገኘው በመመለሷ ተከፋች፡፡
ነገር ግን ነገሩን ስታስበው ጅልነት ሆነባት፡፡ ሰውዬውን ያየችው ለአፍታ ጊዜ ሲሆን በወቅቱም አላነጋገረችውም፡፡ ሆኖም ይህ ሰው ለዓመታት ያጣችውን ፍቅር የሚቀሰቅስባት ሆነባት፡ ታዲያ ይህ ሰውዬ ደግማ ብታገኘው ወይ ባለጌ ይሆናል፣ ወይ ወፈፌ ይሆናል፣ ወይ በሽተኛ
ይሆናል፣ ወይ ደግሞ ገላው የሚቀረና ይሆናል ብላ አሰበች
ከባቡሩ ወርዳ የቤቷን መንገድ ይዛ ስትሄድ ባልጠበቀችው ሁኔታ
ሰውዬው ወደ እሷ ሲመጣ በማየቷ ክው ከማለቷም በላይ ተርበተበተች፡፡
ፊቷ ቲማቲም መሰለ፧ልቧም መቶ ሜትር ሸመጠጠ፡፡ እሱም ሲያያት መደንገጡ ባይቀርም ሊያናግራት ቆም አለ፡፡ እሷ ግን እርምጃዋን ቀጠለች።
አልፋው ስትሄድ ‹‹ነገ ጠዋት ማዕከላዊ መጻሕፍት ቤት ጠብቀኝ›› አለችው
መልስ ይሰጠኛል ብላ ባትጠብቅም ሰውዬው ፈጣን አዕምሮ ያለው መሆኑን በኋላ ተረድታለች፡፡ ወዲያው ‹‹የትኛው ክፍል?›› አላት።
አፏ እንዳመጣላት ‹‹ባዮሎጂ ክፍል›› በማለቷ ሳቅ አለ፡፡
ቤቷ የደረሰችው በደስታ ተሞልታ ነው፡
ቤቱ ውስጥ ሰው የለም፡፡ የፅዳት ሰራተኛዋ ስራዋን ጨራርሳ የሄደች ስትሆን
መርቪን ገና አልገባም፡፡
በማግስቱ ቀጠሯቸው ቦታ መጻሕፍት ቤት ከላይ ‹‹ፀጥታ›› የሚል
ፅሁፍ የተንጠለጠለበት ቦታ ተቀምጦ አገኘችውና ‹‹ሰላም›› ስትለው ሌባ ጣቱን ከንፈሩ ላይ አድርጎ ዝም እንድትልና እንድትቀመጥ አመለከታት
ከዚያ ብጣሽ ወረቀት ላይ አንድ ነገር ፅፎ አቀበላት፡፡ ‹‹ኮፍያሽ ያምራል» የሚል ነበር፡፡ ኮፍያዋን በአንድ በኩል ገደድ አድርጋ ራሷ ላይ የደፋች በመሆኗ የግራ አይኗን ከልሎታል፡፡ ይህ ኮፍያ አደራረግ ፋሽን ሲሆን ይህን ፋሽን ለመከተል የሚደፍሩት ወኔ ያላቸው ጥቂት ሴቶች ብቻ ናቸው።
እስክርቢቶ ከቦርሳዋ አወጣችና ‹‹ኮፍያው ላንተ አይሆንም› ብላ ፅፋ
አሳየችው:፡ እሱም ‹‹የግቢዬን አበባ አስቀምጥበታለሁ›› ብሎ ሲፅፍላት በሳቅ ተንከተከተች፡፡ ‹‹ሽሽሽሽ›› አላት ዝም እንድትል፡
ዳያና ይሄ ሰውዬ ወፈፌ ነው አስቂኝ አለች በሆዷ፡፡ ከዚያ
‹‹ግጥሞችህን ወድጃቸዋለሁ›› ብላ ፃፈችለት፡፡
‹‹እኔም አንቺን ወድጄሻለሁ› ብሎ መለሰላት በፅሁፍ፡፡
‹እብድ› ስትል አሰበች፡፡ ሆኖም እምባዋ በዓይኗ ተንቆረዘዘ፡፡
‹‹ስምህን እንኳን አላውቀውም› ብላ ፃፈችለት።
ቢዝነስ ካርድ አወጣና ሰጣት፡፡ ስሙ ማርክ አልደር ሲሆን የሚኖረው ሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ ነው፡፡
የምሳ ሰዓት ሲደርስ ምሳ ለመብላት ወደ ምግብ ቤት ሄዱ፡ ይህን ሰዓት የመረጠችው ባሏ እንዳያገኛት ነው መቼም በዚህ ሰዓት ባሏ
አይመጣም ብላ፡፡
ከምሳ በኋላ የሙዚቃ ድግስ ለማየት ቴያትር ቤት ገቡ፡፡
ያን ቀን ማርክ የሬዲዮ ኮሜዲ ደራሲ መሆኑን፣ ለታዋቂ ኮሜዲያኖች
እንደሚደርስ፣ እንዲሁም የሬዲዮ ጣቢያ ባለቤት መሆኑን አጫወታት
እንግሊዝ አገር የመጣው ትውልዳቸው ከሊቨርፑል
ውስጥ የሚሳብ የትውልድ ዘር ሐረጎችን ለማፈላለግ መሆኑን ነገራት፡፡
ማርክ አልደር ቁመቱ አጠር ያለ ሲሆን ከዳያና አይበልጥም፧ በእሜም እኩያዋ ነው፡፡ ፊቱ ሁል ጊዜ ፈገግታ አይለየውም፡፡ በአእምሮ የበሰለ አስቂኝና ተጫዋች ሲሆን ባህሪው ልስልስ ያለ በአለባበሱ ሸጋና ፅዱ ነው የሞዛርትን ሙዚቃ የሚወድ ሲሆን ከሁሉም በላይ ግን ዳያናን ወዷታል።
እስካሁን የምታውቃቸው ወንዶች ገላዋን መተሻሸት የሚወዱ፣ ባሏ መርቪን ጀርባውን ማዞሩን አይተው እንተኛ የሚሏት፣ በመጠጥ የደነበዙና ካንቺ ፍቅር ይዞናል እያሉ የሚቀባጥሩ ዓይነት ናቸው፡:
መቼም እሷን ሳይሆን ገላዋን እንደሚፈልጉ ታውቃለች፡፡ ንግግራቸው
የማይጥም ፍሬፈርስኪ ሲሆን እሷ የምትለውን ለመስማት አይፈልጉም፡፡
ስለእሷም ማወቅ ችግራቸው አይደለም:: ማርክ ግን ከነሱ ለየት ያለ ሰው መሆኑን ከቀን ወደ ቀን ማወቅ ችላለች፡፡
መጻሕፍት ቤት በተገናኙ ማግስት መኪና ተከራየና ባህሩ ዳርቻ ወስዶ
አዝናናት፤ ሳንድዊች ጋበዛትና ከለል ያለ ቦታ ፈልገው ተሳሳሙ፡፡
ማርክ ሚድላንድ ሆቴል አልጋ የያዘ ቢሆንም ዳያና እዚያ በጣም ታዋቂ በመሆኗ ከሱ ጋር መግባት አትችልም፡፡ ከምሳ በኋላ እዚያ ከወንድ ጋር ስትገባ ብትታይ በመክሰስ ሰዓት ወሬው በከተማው በሙሉ ይዳረሳል፡በመሆኑም የማርክ ፈጣን አዕምሮ አንድ ነገር ዘየደ፡፡ ሌላ የባህር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ከተማ በመኪና ሄደው ሻንጣ አንጠልጥለው ሆቴል ደረሱና አቶ እና ወይዘሮ አልደር ብለው ተመዝግበው አልጋ ያዙ፡፡ ከዚያም ምሳ በሉና አልጋ ላይ ወጡ፡፡
ማርክ በፀጥታ ልብሱን ማወላለቅ ጀመረ፡፡ እሷ ደግሞ እፍረት ስለያዛት
ልብሷን ያወላለቀችው በሳቅ እየተንከተከተች ነው፡፡
ይወደኝ ይሆን ብላ አልተጨነቀችም፡፡ ከመውደድም እንደሚያመልካት
አውቃለች፡፡ እሱም ጥሩ ሰው በመሆኑ አልተረበሸችም
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ማርክ አልደር በመጀመሪያ ዳያና ላቭሴይንን ያያት ጊዜ ‹‹የአምላክ ያለህ! እንዳንቺ የምታምር ሴት አይቼ አላውቅም›› አላት፡፡
ያገኛት ሁሉ እንዲህ ይላታል፡፡ ዲያና ያለጥርጥር ውብ ሴት ስትሆን ጥሩ ጥሩ ልብስ መልበስም ትወዳለች፡፡ የዚያን ቀን እጀ ጉርድ ቅልጥሟ ጋ የሚደርስ ቀሚስ ለብሳ ነበር፡፡ እንዳማረባትም አውቃለች።
ማንቼስተር ከተማ ሚድላንድ ሆቴል ውስጥ ራት ግብዣ ተጠርታለች
በግብዣው ላይ ከነበሩት ከባሏ የንግድ ሸሪኮች ጋር በሙሉ ስትደንስ አመሸች ታዲያ ሁሉም አብረዋት የደነሱት ወንዶች ደረታቸው ላይ ይለጥፏታል ወይም እግሯ ላይ ይቆማሉ ሚስቶቻቸው ደግሞ በጥላቻ ዐይን አፈር ድሜ ያስግጧታል፡ ወንዶች ቆንጆ ሴት አይተው ሲቅበጠበጡ
ሚስቶች ለምን ባሎቻቸውን ትተው ሴቷ ላይ በቁጣ እንደሚያፈጡ ሁልጊዜ
ይገርማታል፡፡ እሷ እንደሆነ እነዚህን ጉረኛና በዊስኪ የደነበዙ ባሎቻቸውን
አትፈልግም፡፡
አንድ ጊዜማ የከተማውን ምክትል ከንቲባ በሰው ፊት በማዋረዷ ባሏን አሳፍራው ነበር፡ በኋላም ትንሽ እረፍት አገኝ ብላ ሲጋራ የምትገዛ መስላ ከሆቴሉ ወጥታ ሄደች፡
ኮኛኩን እየተጎነጨ ብቻውን ተቀምጧል። ልክ በክፍሉ ውስጥ የፀሃይ ብርሃን የፈነጠቀች ይመስል ስትገባ ዓይኑን ተከለባት፡ ሰውዬው አጠር ያለና እንደ ህፃን ፍልቅልቅ ያለ ፈገግታ የተላበሰ ሲሆን አሜሪካዊ መሆኑ ሁኔታው ያሳብቅበታል፡፡ ገና እንዳያት አድናቆቱን የገለፀላት ሲሆን ሰውዬው የደስ ደስ ያለው በመሆኑ ፈገግ ብትልለትም አላናገረችውም፡፡ ሲጋራዋን
ገዝታ ቀዝቃዛ ውሃ በጉሮሮዋ ለቀቀችና ወደ ዳንሱ አዳራሽ ተመለሰች፡
ሰውዬው ማን እንደሆነች ከቡና ቤቱ አስተናጋጅ ጠየቀና አድራሻዋን
እንደምንም አግኝቶ የፍቅር ግጥም ፅፎ ላከላት፡፡ ግጥሙን ስታነብ አነባች፡፡
ያስለቀሳት ብዙ ነገር ተመኝታ ሁሉንም ነገር ባለማግኘቷ ነው፡፡ ያለቀሰችው በዚች ደስታ በራቃት ከተማ የዓመት እረፍት መውጣት ከሚጠላ ባሏ ጋር ተጣብቃ በመቅረቷ ነው፡፡ ያለቀሰችው ከአምስት ዓመት ወዲህ ለመጀመሪያ
ጊዜ የፍቅር ግጥም በመስማቷ ነው: ያለቀሰችው ለመርቪን ያላት ፍቅር የተሟጠጠ በመሆኑ ነው፡፡
በነጋታው እሁድ ስለነበር ዳያና ቤቷ ውስጥ መሸገች፡፡ ሰኞ ዕለት ወደ
ከተማው መጽሐፍ ቤት ሄዳ ከዚህ ቀደም የተዋሰችውን መጽሐፍ መለሰችና ፊልም ቤት ገባች፡፡ ከዚያም ለእህቷ ልጆች ስጦታ ስትገዛ ዋለች፡፡ በኋላም
እራት መስሪያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ገዛችና ከከተማ ወጣ ወዳለው መኖሪያዋ
በጊዜ ለመድረስ ባቡር ላይ ተሳፈረች፡፡ ከተማ ውስጥ ስትዟዟርና ቡና ስትጠጣ የአሜሪካዊ አነጋገር ቅላፄ ያለውን ሰው ሳታገኘው በመመለሷ ተከፋች፡፡
ነገር ግን ነገሩን ስታስበው ጅልነት ሆነባት፡፡ ሰውዬውን ያየችው ለአፍታ ጊዜ ሲሆን በወቅቱም አላነጋገረችውም፡፡ ሆኖም ይህ ሰው ለዓመታት ያጣችውን ፍቅር የሚቀሰቅስባት ሆነባት፡ ታዲያ ይህ ሰውዬ ደግማ ብታገኘው ወይ ባለጌ ይሆናል፣ ወይ ወፈፌ ይሆናል፣ ወይ በሽተኛ
ይሆናል፣ ወይ ደግሞ ገላው የሚቀረና ይሆናል ብላ አሰበች
ከባቡሩ ወርዳ የቤቷን መንገድ ይዛ ስትሄድ ባልጠበቀችው ሁኔታ
ሰውዬው ወደ እሷ ሲመጣ በማየቷ ክው ከማለቷም በላይ ተርበተበተች፡፡
ፊቷ ቲማቲም መሰለ፧ልቧም መቶ ሜትር ሸመጠጠ፡፡ እሱም ሲያያት መደንገጡ ባይቀርም ሊያናግራት ቆም አለ፡፡ እሷ ግን እርምጃዋን ቀጠለች።
አልፋው ስትሄድ ‹‹ነገ ጠዋት ማዕከላዊ መጻሕፍት ቤት ጠብቀኝ›› አለችው
መልስ ይሰጠኛል ብላ ባትጠብቅም ሰውዬው ፈጣን አዕምሮ ያለው መሆኑን በኋላ ተረድታለች፡፡ ወዲያው ‹‹የትኛው ክፍል?›› አላት።
አፏ እንዳመጣላት ‹‹ባዮሎጂ ክፍል›› በማለቷ ሳቅ አለ፡፡
ቤቷ የደረሰችው በደስታ ተሞልታ ነው፡
ቤቱ ውስጥ ሰው የለም፡፡ የፅዳት ሰራተኛዋ ስራዋን ጨራርሳ የሄደች ስትሆን
መርቪን ገና አልገባም፡፡
በማግስቱ ቀጠሯቸው ቦታ መጻሕፍት ቤት ከላይ ‹‹ፀጥታ›› የሚል
ፅሁፍ የተንጠለጠለበት ቦታ ተቀምጦ አገኘችውና ‹‹ሰላም›› ስትለው ሌባ ጣቱን ከንፈሩ ላይ አድርጎ ዝም እንድትልና እንድትቀመጥ አመለከታት
ከዚያ ብጣሽ ወረቀት ላይ አንድ ነገር ፅፎ አቀበላት፡፡ ‹‹ኮፍያሽ ያምራል» የሚል ነበር፡፡ ኮፍያዋን በአንድ በኩል ገደድ አድርጋ ራሷ ላይ የደፋች በመሆኗ የግራ አይኗን ከልሎታል፡፡ ይህ ኮፍያ አደራረግ ፋሽን ሲሆን ይህን ፋሽን ለመከተል የሚደፍሩት ወኔ ያላቸው ጥቂት ሴቶች ብቻ ናቸው።
እስክርቢቶ ከቦርሳዋ አወጣችና ‹‹ኮፍያው ላንተ አይሆንም› ብላ ፅፋ
አሳየችው:፡ እሱም ‹‹የግቢዬን አበባ አስቀምጥበታለሁ›› ብሎ ሲፅፍላት በሳቅ ተንከተከተች፡፡ ‹‹ሽሽሽሽ›› አላት ዝም እንድትል፡
ዳያና ይሄ ሰውዬ ወፈፌ ነው አስቂኝ አለች በሆዷ፡፡ ከዚያ
‹‹ግጥሞችህን ወድጃቸዋለሁ›› ብላ ፃፈችለት፡፡
‹‹እኔም አንቺን ወድጄሻለሁ› ብሎ መለሰላት በፅሁፍ፡፡
‹እብድ› ስትል አሰበች፡፡ ሆኖም እምባዋ በዓይኗ ተንቆረዘዘ፡፡
‹‹ስምህን እንኳን አላውቀውም› ብላ ፃፈችለት።
ቢዝነስ ካርድ አወጣና ሰጣት፡፡ ስሙ ማርክ አልደር ሲሆን የሚኖረው ሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ ነው፡፡
የምሳ ሰዓት ሲደርስ ምሳ ለመብላት ወደ ምግብ ቤት ሄዱ፡ ይህን ሰዓት የመረጠችው ባሏ እንዳያገኛት ነው መቼም በዚህ ሰዓት ባሏ
አይመጣም ብላ፡፡
ከምሳ በኋላ የሙዚቃ ድግስ ለማየት ቴያትር ቤት ገቡ፡፡
ያን ቀን ማርክ የሬዲዮ ኮሜዲ ደራሲ መሆኑን፣ ለታዋቂ ኮሜዲያኖች
እንደሚደርስ፣ እንዲሁም የሬዲዮ ጣቢያ ባለቤት መሆኑን አጫወታት
እንግሊዝ አገር የመጣው ትውልዳቸው ከሊቨርፑል
ውስጥ የሚሳብ የትውልድ ዘር ሐረጎችን ለማፈላለግ መሆኑን ነገራት፡፡
ማርክ አልደር ቁመቱ አጠር ያለ ሲሆን ከዳያና አይበልጥም፧ በእሜም እኩያዋ ነው፡፡ ፊቱ ሁል ጊዜ ፈገግታ አይለየውም፡፡ በአእምሮ የበሰለ አስቂኝና ተጫዋች ሲሆን ባህሪው ልስልስ ያለ በአለባበሱ ሸጋና ፅዱ ነው የሞዛርትን ሙዚቃ የሚወድ ሲሆን ከሁሉም በላይ ግን ዳያናን ወዷታል።
እስካሁን የምታውቃቸው ወንዶች ገላዋን መተሻሸት የሚወዱ፣ ባሏ መርቪን ጀርባውን ማዞሩን አይተው እንተኛ የሚሏት፣ በመጠጥ የደነበዙና ካንቺ ፍቅር ይዞናል እያሉ የሚቀባጥሩ ዓይነት ናቸው፡:
መቼም እሷን ሳይሆን ገላዋን እንደሚፈልጉ ታውቃለች፡፡ ንግግራቸው
የማይጥም ፍሬፈርስኪ ሲሆን እሷ የምትለውን ለመስማት አይፈልጉም፡፡
ስለእሷም ማወቅ ችግራቸው አይደለም:: ማርክ ግን ከነሱ ለየት ያለ ሰው መሆኑን ከቀን ወደ ቀን ማወቅ ችላለች፡፡
መጻሕፍት ቤት በተገናኙ ማግስት መኪና ተከራየና ባህሩ ዳርቻ ወስዶ
አዝናናት፤ ሳንድዊች ጋበዛትና ከለል ያለ ቦታ ፈልገው ተሳሳሙ፡፡
ማርክ ሚድላንድ ሆቴል አልጋ የያዘ ቢሆንም ዳያና እዚያ በጣም ታዋቂ በመሆኗ ከሱ ጋር መግባት አትችልም፡፡ ከምሳ በኋላ እዚያ ከወንድ ጋር ስትገባ ብትታይ በመክሰስ ሰዓት ወሬው በከተማው በሙሉ ይዳረሳል፡በመሆኑም የማርክ ፈጣን አዕምሮ አንድ ነገር ዘየደ፡፡ ሌላ የባህር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ከተማ በመኪና ሄደው ሻንጣ አንጠልጥለው ሆቴል ደረሱና አቶ እና ወይዘሮ አልደር ብለው ተመዝግበው አልጋ ያዙ፡፡ ከዚያም ምሳ በሉና አልጋ ላይ ወጡ፡፡
ማርክ በፀጥታ ልብሱን ማወላለቅ ጀመረ፡፡ እሷ ደግሞ እፍረት ስለያዛት
ልብሷን ያወላለቀችው በሳቅ እየተንከተከተች ነው፡፡
ይወደኝ ይሆን ብላ አልተጨነቀችም፡፡ ከመውደድም እንደሚያመልካት
አውቃለች፡፡ እሱም ጥሩ ሰው በመሆኑ አልተረበሸችም
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሻንቆና ከላላ የተሰባሰቡት ሽማግሎች በደልቲ ገልዲና በካርለት ጋብቻ ላይ ሸንጎ ከመቀመጣቸው በፊት በኅብረተሰቡ አጋጣሚ ላይ
ትንበያ መስጠት ይችላሉ የተባሉት፣ «ጫማ ጣዮች» ደጋግመው ጫማ በመጣል ጋብቻው ስለ መሥመሩ አስተያየታቸውን ሰጡ"
ከጫማ ጣዮቹ ቀጥሎ ደግሞ ፍየል ታርዶ «ለአንጀት አይታዎች» ቀርቦ ጋብቻውን በተመለከተ እነሱም አስተያየት እንዲሰጡ ተጠየቁ። እነሱም ተጋቢዎቹ ልጅ ስለ መውለድ አለመውለዳቸው
ሊታያቸው ባለመቻሉ ሦስት ፍየል ከታረደ በኋላ፣ «ጋብቻው ቀና ነው» በሚል ብቻ አድበስብሰው ተውት"
በእርግጥ፣ ይህ ጉዳይ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ያወያየ ሲሆን፣ በተለይም በሽማግሎቹ ዘንድ ጋብቻውን በመጠራጠር በቀጠሮ በተለያየ ጊዜያት ለመወያየት አስቻላቸው"
ካርለት አንጀት አይታዎች በሰጡት አስተያየት መደናገጧና መደነቋ አልቀረም" በሐመር ማኅበረሰብ መካን ሴት ፈላጊ እንደ ሌላት ታውቃለች" አንድ ሴት ለአባቷ ጥሎሽ ተከፍሎ ባሏ ዘንድ ከሄደች በኋላ ልጅ ሳትወልድ ብትቀር ባሏ እሷን መልሶ ታናሿን፣
ካለበለዚያም ቅርብ ዘመዷን ያገባል" ያም ሆኖ ካልተሳካለት፣ ልጅ
መውለድ ካልቻለች ላባቷ የከፈለውን ጥሎሽ ያስመልሳል ሴቷም፣
«መካን የሆነችው በውኃ ብልቷን ታጥባ ይሆናል» ተብላ ትጠረጠራለች» መካን ሴት የተገኘችበት ቤተሰብም እንደ መጥፎ
ቤተሰብ ስለሚቈጠር ጋብቻ የሚፈልገው ሁሉ ይሸሻል" ይህ ደግሞ አባት በልጆቹ ጥሎሽ ያገኘው የነበረውን ከብት፣ ፍየል፣ በግ፣ ማር
ያስቀርበታል" ከዚያም ተጨማሪ፣ ምናልባት አባትየው ሦስት ሴት
ልጆች ቢኖሩት የመጀመሪያ ልጁን ጥሎሽ ተቀብሎ ቢድርና መካን ብትሆን ሁለተኛዋን፣ ሁለተኛዋም መካን ከሆነች ሦስተኛዋን! |
ሦስተኛዋ መካን ከሆነች የዘመድ ልጅ...በመስጠት ሞክሮ ካልተቻለ ግን የተቀበለውን ጥሎሽ ይመልሳል"
«ስለዚህ አንደኛ ነገር እኔ በውኃ ስተጣጠብ ስለሚያዩ መካን ትሆናለች የሚል ግምት መጀመሪያውንም ነበራቸው" ሁለተኛ ደግሞ
አንጀት አይታዎችና ጫማ ጣይዎች ልጅ ልወልድ አለመቻሌን ለማኅበረሰቡ አስታውቀዋል። ሌላው ግን የኔው የራሴ ጉዳይ ነው
ለጥንቃቄ እንዳላረግዝ የሕክምና መከላከያ አለኝ" ስለዚህ ልወልድ
አለመቻሌን አውቀዋለሁ" እነሱም ባለመውለዴ እጅግ በጣም አምነዋል" ግንኮ እንዴት? የፍየል አንጀት ከኔ ጋር ምን አገናኘው ካርለት፣ ራሷ ለራሷ ሐሳቧን አካፍላ ራሷን ጠየቀች።
ካርለት በእውነቱ ከሆነ ጥሎሽ ከደልቲ ገልዲ ማግኘት አትሻም
ጥሎሽ አያስፈልግም ብትል ግን የሱ የግል ንብረትነቷ ማረጋገጫ አጣ ማለት ነው" ጋብቻው ከዚህ ሁሉ ቢቀርስ እንዳይባል ደግሞ እሷ ባህላዊ ግድቡን ጥሳ ጥናቷን ለማካሄድ፣ ደልቲ ደግሞ ባለጌዋን እንግዳ የራሱ አድርጎ በግርፋት ሥነ ሥርዓትንሊያስትምራት
ቈርጧል።
በግልና በተናጠል የላላና ሻንቆ ኗሪ ሲመክርና ለሽማግሎቹ
የመሰለውን አስተያየት ሲሰጥ ሰንብቶ በመጨረሻ ሽማግሎቹ በጥልቅ ከተመካከሩ በኋላ
«እንግዳዋ ምንም እንኳ በመልክና በቋንቋዋ ከእኛ ብትለይም የቦርጆ (የአምላካችን) ፍጡር ናት። እኛን ብላ፣ እኛን መርጣ መጣች እንጂ ማሌ፣ በና፣ ዳሳነች፣ ሙርሲ...ምድር ልትሄድ ይቻላት ነበር።
በእውነት ከሆነ ብልግናዋ የበዛ ነው" ይህ ደግሞ የሷ ስሕተት ሳይሆን፣ ያባቷ ስሕተት ነው» ብለው ጋብቻውን ለመቀበል ወሰኑ።
በመቀጠልም፣ «ይህች እንግዳ አባቷ በቅርብ ባለመኖሩ ደልቲ ገልዲ የሚከፍለውን ጥሎሽ የሚቀበል አባትና ጥሎሹን የሚወስን ሰው የላትም" ስለዚህ እሷ የፈለገችውን ሰው በአባትነት ትምረጥ።
ከእንግዲህ በኋሳ የምትለብሰው፣ ጠረኗ እንደ ሐመር ልጃገረዶች
እንዲሆንና እስከ አሁን የፈጸመችውን ስሕተት እሷም ራሷ ስለምታውቅ ለወደፊት የፍየል ቆዳ ለፍቶና ተሰፍቶ እንድትለብስ፣በጨሌና አንባር በማጌጥም ጸጕሯን አጠር አድርጋ አስቈርጣ ሹርባ እንድትሠራና በእግሯ እንድትሄድ» ብለው ተስማሙ"
«ባባቷ በባንኪ ሞሮ ደንብ መሠረትም ጥሩ ሴት ለመባል አባት ብላ ለምትመርጠው ወንድ ልጅ ወይም በዘመዱ ወንድ ልጅ የከብትጨዝላይ ወቅት በባራዛ አርጩሜ ዱላ ቻይ መሆኗን ለማስመስከር
ላትሸማቀቅ ፀንጋዞች (ባዕዳን) በሚባሉት ጐረምሶች እንድትገረፍና
ጀርባዋ ላይ የሚቀረው የግርፋት ምልክት ለሽማግሎችና ለአካባቢው ሰው እንዲታይ በግልጽ እንድትተወውና እንድታጌጥበት»
ተባብለው ተማመኑ።
ከሎ ሆራ የሽማግሎችን ሁኔታና አጠቃላይ ውሳኔያቸውን ለካርለት ሲነግራት ጥርሷ እስኪፋጭ ድረስ ተንቀጠቀጠች" መናገር †ሳናት" በእውነቱ ለተመለከታት የማንኛውንም ሰው አንጀት የምትበላ ሲሆን፣ በሌላ በኩልም ጋብቻ ለመፈጸም ማሰብ የግብዝነት ተግባር ነው ሊያሰኝ የሚችል ነበር።
ካርለት ከከሎ ተለይታ ሰቀላዋ ውስጥ ገብታ ምን እያደረገችና ወደፊትስ ምን ሊያጋጥማት እንደሚችል ስታስብ፣ እንባዋ
እየተንፎለፎለ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ከዚህ ቀደም የኖረችበት ዓለም
እውነት አሁን ባለችበት መሬት ላይ ሳይሆን ከሌላ ፈለክ (ፕላኔት) የመጣች እንግዳ ፍጡር የሆነች መሰላት" ሽማግሎቹ ካቀረቡላት ቅድመ ሁኔታና ባህላዊ የውጣ ውረድ ይልቅ በትንሿ የመርፌ
ቀዳዳ ሾልኮ ማለፍ እንደሚሻል ገመተች"
እሷ የምታውቀው ሕይወትና አሁን ያለችበት ዓለም የሰማይና የምድር ያህል ይራራቃል ተብሎ በርቀት ልዩነት ብቻ የሚለካ
ሳይሆን፣ ፈጽሞ ሊተያይ የማይችል ሆድና ጀርባ ሆነባት"
ግርፊያ.ቆዳ መልበስ…በባዶ እግር መሄድ ...አለመታጠብ ልት
ረዳው፣ልታምነው፣
ልትሰማማው የማትፈልገው ጉዳይ ነው።ስለሆነም ይህን ፈጽሚ ማለት፣ በሷ ላይ ትልቅ ችግር መፍጠር ብቻ ሳይሆን ይቅር የማይባል ግፍ እንደ መፈጸም ያክል ነው" አባባሉን እንኳን በተግባር በቃል ልትሰማው ከበዳት።
ታላቁ የሴቶች እንቅስቃሴ ለመላው አውሮፓ ሴቶች ያጎናጸፈው መብት ብናኙ እንኳን ወደማይገኝበት መጥታ መገኘቷ፣ ከመላ ሴቶች ጎን ተነጥላ ወደ ዘንዶ አፍ የመወርወር ያህል ሆኖ ተሰማት ስለዚህ ለምን ወደዚህ ጣጣ ራሷን እንደዶለች ማሰላሰል
ጀመረች ካርለት ፍዝዝ፣ ትክዝ እያለች ቀስ በቀስ አንገቷን ወደ ሰማይ በማስገግ ወደ አውሮፓ በሐሳብ ተጓዘች።
እናቷ ሚስስ አልፈርድ፣ ታናሽ እኅቷ ሴሻ አጠገቧ ቢኖሩላት ኖሮ ጭንቀቷን ገልጻላቸው ተያይዘው ያለቅሱ ነበር። ግን ምንስ ብላ ልትገልጽላቸው ነው?
«እኔ እራሴ እንኳ ሁኔታዎች ከቍጥጥሬ ውጭ ሆነውብኝ መላ ብዬ የፈጠርኩት እንጂ እነሱማ መጀመሪያውንስ እንዴት ሊረዱኝ ይችላሉ? እናቴና እኅቴ እንዳፈቅር ገፋፍተውኛል" ለታናሽ እኅቴም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ምን ዓይነት የደስታ ስሜት እንደሚፈጥር
የነገርኳት እኔ ነኝ” ጋብቻ ጥንቃቄን የሚጠይቅ ከባድ ነገር መሆኑን እንደሆነ የእንግሊዝ አገር ወጣት በየትምህርት ቤቱ፣ በቲያትርና ሲኒማው የሚያውቀው የአደባባይ ምሥጢር ነው።
«የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፍቅር ዋነኛው ቅመም ቢሆንም በራሱ ግን ፍቅር አይሆንም" ያልተፈለፈለ፣ እዶሮ እቅፍ ውስጥ ያለ እን
ቍላል እንደ ማለት ነው እንቍላሉ ነፍስ ሆኖ ከመፈጠሩ በፊት እን
ስቷ ዶሮና አውራው መገናኘት አለባቸው" የሰዎች ግንኙነት ደግሞ
ከዚህ በላይ ነው" በሐሳብ መጣጣምና መግባባት ያስፈልጋቸዋል"።
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሻንቆና ከላላ የተሰባሰቡት ሽማግሎች በደልቲ ገልዲና በካርለት ጋብቻ ላይ ሸንጎ ከመቀመጣቸው በፊት በኅብረተሰቡ አጋጣሚ ላይ
ትንበያ መስጠት ይችላሉ የተባሉት፣ «ጫማ ጣዮች» ደጋግመው ጫማ በመጣል ጋብቻው ስለ መሥመሩ አስተያየታቸውን ሰጡ"
ከጫማ ጣዮቹ ቀጥሎ ደግሞ ፍየል ታርዶ «ለአንጀት አይታዎች» ቀርቦ ጋብቻውን በተመለከተ እነሱም አስተያየት እንዲሰጡ ተጠየቁ። እነሱም ተጋቢዎቹ ልጅ ስለ መውለድ አለመውለዳቸው
ሊታያቸው ባለመቻሉ ሦስት ፍየል ከታረደ በኋላ፣ «ጋብቻው ቀና ነው» በሚል ብቻ አድበስብሰው ተውት"
በእርግጥ፣ ይህ ጉዳይ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ያወያየ ሲሆን፣ በተለይም በሽማግሎቹ ዘንድ ጋብቻውን በመጠራጠር በቀጠሮ በተለያየ ጊዜያት ለመወያየት አስቻላቸው"
ካርለት አንጀት አይታዎች በሰጡት አስተያየት መደናገጧና መደነቋ አልቀረም" በሐመር ማኅበረሰብ መካን ሴት ፈላጊ እንደ ሌላት ታውቃለች" አንድ ሴት ለአባቷ ጥሎሽ ተከፍሎ ባሏ ዘንድ ከሄደች በኋላ ልጅ ሳትወልድ ብትቀር ባሏ እሷን መልሶ ታናሿን፣
ካለበለዚያም ቅርብ ዘመዷን ያገባል" ያም ሆኖ ካልተሳካለት፣ ልጅ
መውለድ ካልቻለች ላባቷ የከፈለውን ጥሎሽ ያስመልሳል ሴቷም፣
«መካን የሆነችው በውኃ ብልቷን ታጥባ ይሆናል» ተብላ ትጠረጠራለች» መካን ሴት የተገኘችበት ቤተሰብም እንደ መጥፎ
ቤተሰብ ስለሚቈጠር ጋብቻ የሚፈልገው ሁሉ ይሸሻል" ይህ ደግሞ አባት በልጆቹ ጥሎሽ ያገኘው የነበረውን ከብት፣ ፍየል፣ በግ፣ ማር
ያስቀርበታል" ከዚያም ተጨማሪ፣ ምናልባት አባትየው ሦስት ሴት
ልጆች ቢኖሩት የመጀመሪያ ልጁን ጥሎሽ ተቀብሎ ቢድርና መካን ብትሆን ሁለተኛዋን፣ ሁለተኛዋም መካን ከሆነች ሦስተኛዋን! |
ሦስተኛዋ መካን ከሆነች የዘመድ ልጅ...በመስጠት ሞክሮ ካልተቻለ ግን የተቀበለውን ጥሎሽ ይመልሳል"
«ስለዚህ አንደኛ ነገር እኔ በውኃ ስተጣጠብ ስለሚያዩ መካን ትሆናለች የሚል ግምት መጀመሪያውንም ነበራቸው" ሁለተኛ ደግሞ
አንጀት አይታዎችና ጫማ ጣይዎች ልጅ ልወልድ አለመቻሌን ለማኅበረሰቡ አስታውቀዋል። ሌላው ግን የኔው የራሴ ጉዳይ ነው
ለጥንቃቄ እንዳላረግዝ የሕክምና መከላከያ አለኝ" ስለዚህ ልወልድ
አለመቻሌን አውቀዋለሁ" እነሱም ባለመውለዴ እጅግ በጣም አምነዋል" ግንኮ እንዴት? የፍየል አንጀት ከኔ ጋር ምን አገናኘው ካርለት፣ ራሷ ለራሷ ሐሳቧን አካፍላ ራሷን ጠየቀች።
ካርለት በእውነቱ ከሆነ ጥሎሽ ከደልቲ ገልዲ ማግኘት አትሻም
ጥሎሽ አያስፈልግም ብትል ግን የሱ የግል ንብረትነቷ ማረጋገጫ አጣ ማለት ነው" ጋብቻው ከዚህ ሁሉ ቢቀርስ እንዳይባል ደግሞ እሷ ባህላዊ ግድቡን ጥሳ ጥናቷን ለማካሄድ፣ ደልቲ ደግሞ ባለጌዋን እንግዳ የራሱ አድርጎ በግርፋት ሥነ ሥርዓትንሊያስትምራት
ቈርጧል።
በግልና በተናጠል የላላና ሻንቆ ኗሪ ሲመክርና ለሽማግሎቹ
የመሰለውን አስተያየት ሲሰጥ ሰንብቶ በመጨረሻ ሽማግሎቹ በጥልቅ ከተመካከሩ በኋላ
«እንግዳዋ ምንም እንኳ በመልክና በቋንቋዋ ከእኛ ብትለይም የቦርጆ (የአምላካችን) ፍጡር ናት። እኛን ብላ፣ እኛን መርጣ መጣች እንጂ ማሌ፣ በና፣ ዳሳነች፣ ሙርሲ...ምድር ልትሄድ ይቻላት ነበር።
በእውነት ከሆነ ብልግናዋ የበዛ ነው" ይህ ደግሞ የሷ ስሕተት ሳይሆን፣ ያባቷ ስሕተት ነው» ብለው ጋብቻውን ለመቀበል ወሰኑ።
በመቀጠልም፣ «ይህች እንግዳ አባቷ በቅርብ ባለመኖሩ ደልቲ ገልዲ የሚከፍለውን ጥሎሽ የሚቀበል አባትና ጥሎሹን የሚወስን ሰው የላትም" ስለዚህ እሷ የፈለገችውን ሰው በአባትነት ትምረጥ።
ከእንግዲህ በኋሳ የምትለብሰው፣ ጠረኗ እንደ ሐመር ልጃገረዶች
እንዲሆንና እስከ አሁን የፈጸመችውን ስሕተት እሷም ራሷ ስለምታውቅ ለወደፊት የፍየል ቆዳ ለፍቶና ተሰፍቶ እንድትለብስ፣በጨሌና አንባር በማጌጥም ጸጕሯን አጠር አድርጋ አስቈርጣ ሹርባ እንድትሠራና በእግሯ እንድትሄድ» ብለው ተስማሙ"
«ባባቷ በባንኪ ሞሮ ደንብ መሠረትም ጥሩ ሴት ለመባል አባት ብላ ለምትመርጠው ወንድ ልጅ ወይም በዘመዱ ወንድ ልጅ የከብትጨዝላይ ወቅት በባራዛ አርጩሜ ዱላ ቻይ መሆኗን ለማስመስከር
ላትሸማቀቅ ፀንጋዞች (ባዕዳን) በሚባሉት ጐረምሶች እንድትገረፍና
ጀርባዋ ላይ የሚቀረው የግርፋት ምልክት ለሽማግሎችና ለአካባቢው ሰው እንዲታይ በግልጽ እንድትተወውና እንድታጌጥበት»
ተባብለው ተማመኑ።
ከሎ ሆራ የሽማግሎችን ሁኔታና አጠቃላይ ውሳኔያቸውን ለካርለት ሲነግራት ጥርሷ እስኪፋጭ ድረስ ተንቀጠቀጠች" መናገር †ሳናት" በእውነቱ ለተመለከታት የማንኛውንም ሰው አንጀት የምትበላ ሲሆን፣ በሌላ በኩልም ጋብቻ ለመፈጸም ማሰብ የግብዝነት ተግባር ነው ሊያሰኝ የሚችል ነበር።
ካርለት ከከሎ ተለይታ ሰቀላዋ ውስጥ ገብታ ምን እያደረገችና ወደፊትስ ምን ሊያጋጥማት እንደሚችል ስታስብ፣ እንባዋ
እየተንፎለፎለ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች። ከዚህ ቀደም የኖረችበት ዓለም
እውነት አሁን ባለችበት መሬት ላይ ሳይሆን ከሌላ ፈለክ (ፕላኔት) የመጣች እንግዳ ፍጡር የሆነች መሰላት" ሽማግሎቹ ካቀረቡላት ቅድመ ሁኔታና ባህላዊ የውጣ ውረድ ይልቅ በትንሿ የመርፌ
ቀዳዳ ሾልኮ ማለፍ እንደሚሻል ገመተች"
እሷ የምታውቀው ሕይወትና አሁን ያለችበት ዓለም የሰማይና የምድር ያህል ይራራቃል ተብሎ በርቀት ልዩነት ብቻ የሚለካ
ሳይሆን፣ ፈጽሞ ሊተያይ የማይችል ሆድና ጀርባ ሆነባት"
ግርፊያ.ቆዳ መልበስ…በባዶ እግር መሄድ ...አለመታጠብ ልት
ረዳው፣ልታምነው፣
ልትሰማማው የማትፈልገው ጉዳይ ነው።ስለሆነም ይህን ፈጽሚ ማለት፣ በሷ ላይ ትልቅ ችግር መፍጠር ብቻ ሳይሆን ይቅር የማይባል ግፍ እንደ መፈጸም ያክል ነው" አባባሉን እንኳን በተግባር በቃል ልትሰማው ከበዳት።
ታላቁ የሴቶች እንቅስቃሴ ለመላው አውሮፓ ሴቶች ያጎናጸፈው መብት ብናኙ እንኳን ወደማይገኝበት መጥታ መገኘቷ፣ ከመላ ሴቶች ጎን ተነጥላ ወደ ዘንዶ አፍ የመወርወር ያህል ሆኖ ተሰማት ስለዚህ ለምን ወደዚህ ጣጣ ራሷን እንደዶለች ማሰላሰል
ጀመረች ካርለት ፍዝዝ፣ ትክዝ እያለች ቀስ በቀስ አንገቷን ወደ ሰማይ በማስገግ ወደ አውሮፓ በሐሳብ ተጓዘች።
እናቷ ሚስስ አልፈርድ፣ ታናሽ እኅቷ ሴሻ አጠገቧ ቢኖሩላት ኖሮ ጭንቀቷን ገልጻላቸው ተያይዘው ያለቅሱ ነበር። ግን ምንስ ብላ ልትገልጽላቸው ነው?
«እኔ እራሴ እንኳ ሁኔታዎች ከቍጥጥሬ ውጭ ሆነውብኝ መላ ብዬ የፈጠርኩት እንጂ እነሱማ መጀመሪያውንስ እንዴት ሊረዱኝ ይችላሉ? እናቴና እኅቴ እንዳፈቅር ገፋፍተውኛል" ለታናሽ እኅቴም የግብረ ሥጋ ግንኙነት ምን ዓይነት የደስታ ስሜት እንደሚፈጥር
የነገርኳት እኔ ነኝ” ጋብቻ ጥንቃቄን የሚጠይቅ ከባድ ነገር መሆኑን እንደሆነ የእንግሊዝ አገር ወጣት በየትምህርት ቤቱ፣ በቲያትርና ሲኒማው የሚያውቀው የአደባባይ ምሥጢር ነው።
«የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፍቅር ዋነኛው ቅመም ቢሆንም በራሱ ግን ፍቅር አይሆንም" ያልተፈለፈለ፣ እዶሮ እቅፍ ውስጥ ያለ እን
ቍላል እንደ ማለት ነው እንቍላሉ ነፍስ ሆኖ ከመፈጠሩ በፊት እን
ስቷ ዶሮና አውራው መገናኘት አለባቸው" የሰዎች ግንኙነት ደግሞ
ከዚህ በላይ ነው" በሐሳብ መጣጣምና መግባባት ያስፈልጋቸዋል"።
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ከፖርት ፕሪንስ በስተ ምስራቅ ፓርቶሪኮ ሳንጁአን ውስጥ የግል እርሻ የጀመረው አሌክስ ቀደም ሲል የስፔን ፋሽዝም
አራማጅና የጦር አባል ከነበረው ስመ ጥር አባቱ ጋር ወደ ፓርቶሪ
በተደጋጋሚ ከሄደ በኋላ ሳንጁአን ለመኖር እንዲወስን ተፈጥሮአዊ
ፍቅሩ አደፋፈረው፡
የሻምበልነት ማዕረግ የነበረው አባቱ ልጁ በእርሻ ትምህርት ሰልጥኖ ህይወቱ በእርሻ ምርት ላይ ቢመሰረት የወደፊት ዕድሉ
የተቃና ደስተኛና ሃብታም ሊሆን እንደሚችል በመከረው መሰረት
አሴክስ የአባቱን ህልም የእራሱ በማድረግ ህልሙን ለማሳካት የሚያስችለውን ጥረት ፈጽሞ በመጨረሻ ተሳካለት፡
አሌክስ ደጋግሞ ስለ እርሻ ዘመናዊ እርሻ ስለሚያስገኘው
ብልፅግና ስለ ተሻሉ የምርት ውጤቶች ማውራት እንጂ በፍቅሩ ተረትታ
እንደነፍስ ጡር ለምትብረከረከው
ፍቅረኛው ቁብ
አልነበረውም ሌላው ቀርቶ እግሩ ስር እንደምትታከከውና "ፔሙስ" ብሎ እንደሚጠራት ድመቱ ሲገናኙ እጁን ሰዶ ዳብሷት ካልያም እጆችዋን ስቦ ወደ ደረቱ አስጠግቷት አያውቅም አይብዛ እንጂ
አንድ ወቅት የፍቅር አባባሎችን ይለዋወጡ አብረውም እየተሻሹ
ጊዜያቸውን በደስታ ያሳልፉ የነበረ ቢሆንም! ያ የስሜት መመሳሰል ግን ከጠለቀ ብዙ ወራቶች ተቆጠሩ።
ይህ የቸልተኝነት ባህሪው ሸበላ ቁመናው የታከታት ደረቅ የአጨዋወት ስልቱ ሳይቀር አኜስን ለአሌክስ ያላትን ስሜት ከእለት
ወደ እለት እንዲያድግ አደረገው። አንዳንዴ እንዲያውም፡-
“አሌክስ! እባክህ ለፍቅራችን የሚሆን ጊዜ ይኑርህ? እባክህ በፍቅር
ስሜቴ አትጫወትበት!...” በማለት ምርር ብላ ስትነግረው፡-
“እባክሽ አኜስ ታገሽ!
ትዕግስት ይኑርሽ! ልትረጅኝ
ሞክሪ! በአሁኑ ሰዓት የፍቅር ስሜቴ በወደፊት ዓላማዬ እንደ ጉም ተሸፍኗል። አንድ ወቅት ግን ጉሙ ይበተናል፤ በሰማያዊው ሰማይ
ከምስራቅ ወደ ምዕራብ እንደምትጓዝ ፀሐይ የፍቅር ብርሃን ፍንትው ብሎ ይፈነጥቃል...'' ይላታል:
“አሌክስ! እኔ'ኮ ብዙ ላሳስብህ አልሻም። በሳምንት ቢያንስ
ለተወሰነ ደቂቃ እንኳ ፍቅር እንድንለዋወጥ ለማድረግ ሞክር ፧እየተጎዳሁ ነው” ስትለው፡-
“እስኪ እሞክራለሁ አንች ግን ጠንከር በይ: በህልሜ
ልትደሰች ሞክሪ በአትላንቲክ ውቅያኖስ በተከበበችው ሳን ጁን
ውስጥ የሚኖረው ቡቃያ ንፋሱ ጎንበስ ቀና ሲያደርገው ይታይሽ!
አዲዎስ ብሏት ይሄዳል።
አንድ ቀን ግን አሌክስ በጅፕ መኪናው መኖሪያዋ ድረስ መጥቶ ድንገት “ለሽርሽር እንሂድ? አላት።
“የት?” አለችው አኜስ ግራ ተጋብታ።
“ሱ..” አለ አፉን በቀኝ እጁ አመልካች ጣት እየጠበጠበ።
“አሌክስ የት እንደምንሄድ መንገሩን ባትፈልግ እንኳን ወጣ እንደምንል ቀደም ብለህ ፍንጭ መስጠት ነበረብህ: ከሰዓታት
ወይንም ከቀናት በፊት ወጣ እንደምንል ነግረኸኝ ቢሆን ኖሮ ነፍሴ በደስታ ከመዝለሏም በተጨማሪ ስሜቴ በጉጉት ተበረጋግዶ በናፍቆት ይጠብቅህ ነበር: አሁን ግን ልቤ በሐዘን ቀዝቅዛለች። ስሜቴም በድን
ነው። እኔም ስላልተዘጋጀሁ የትም መሄድ አልፈልግም” አሰችው።
ያልተለመደ ፈገግታ አሳይቶ ባልጠበቀችው መልክ የግራ እጅዋን ብድግ አድርጎ ጣቶችዋን ሳም ሳም አደረጋት፤ ጉንጯን በቀኝ
እጅ አመልካች ጣቱ ደባበሰላት: ሽቅብ አንስቶም ከንፈሯን በከንፈሩ
ደባበሰላት።
ወዲያው ልቧ ጋለች ሰውነቷ በሙቀት ተጥለቀለቀ፡
የፍቅር ሃይሏ ከየስርቻው ተሰባሰበ ስለዚህ! “ማሬ!
እንሂድ" አለችው::ሃሳቡን እንዳይለወጥ እየሰጋች: አሌክስ መኪናውን እያሽከረከረ ጭኖችዋን በቀኝ እጁ እየደባበሰ የምትሆነውን አሳጣት: ያ ጨካኙ አሌክስ ሳይሆን የፍቅር መልአክ ሆነባት…
“አሌክስ አልቻልሁም አለችው እየተስለመለመች
ጥቂት ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ።
“ትዕግስት ጥሩ ነው..."
“ኡፍ ስብከትህን አቁም። በሰዎች ሙያ ጣልቃ አትግባ መኪናዋን ይልቁንስ አቁም አለችው በትዕዛዝ መልክ፡ መኪናዋ ወደ
ዳር ወጥታ ቆመች ሞተሯ ጠፋ።
ከተቀመጠችበት ዞር ብላ እጆችዋን ዘርግታ የአሌክስን
አንገት አቀፈችው። ተገናኙ
ረሃብተኛዋ ከንፈሩን ጎረሰቸው እፅዋት በነፋሱ ጎንበስ ቀና ይላሉ ከርቤው እየጤሰ መላዕክት
እያጀቧቸው ሽቅብ በፍቅር ስረገላ አረጉ።
“አሌክስ! እኔ አላምንም... እንዴት ደስ አለኝ ለካ እንዲህ የደስታ ምንጭ ነህ እሰይ እንኳን ታገስኩህ እንኳን ቻልኩህ እንግዲህ ዳግመኛ ከፍቅር ሠረገላችን አንወርድም አይደል! ከምድር ላይ ይልቅ እዚህ ነፍስ ነህ..." እያለች ላዩ ላይ ተንከባለለችበት
የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል በርቀት ከቆሙት መርከቦችና አጠገባቸው ካለው የድንጋይ ግንብ ጋር እየተላተመ አረፋ ሲደፍቅ
ከኮሎምበስ መታሰቢያ ግዙፍ ሃውልት ትይዩ የሚነፍሰው ጤሮ ንፋስ በጆሮ ግንዷ እያፋጨ ሲያልፍ ግን አይኗን ገልጣ ከገነት ወደ ምድር ተመለሰች። ምድሯን ውቅያኖሱን ስታይ አስጠሏት፡ አሌክስ
አሁንም አብሯት አለ ያ ሲያደርጉ የነበረውና አሁን አጠገቧ ባለው አሌክስ መካከል ግን ልዩነት ያለ መሰላት፤ ተጠራጠረችው።
“ማሬ የት ነው ያለነው?" ከሰመመኗ እንደነቃች ጠየቀችው።
“ሁዌልቫ ነን! ለስንብት አመች በመሆኗ የምሄድበትንም ከርቀት ላሳይሽ ስለምችል ሁዌልቫን መርጨልሻለሁ" አላት ሳብ አድርጎ ወርቃማ ዞማ ፀጉሯን ስሞ፡
“ሁዌልቫ” ይህ ስም ምድር ላይ ያውም ስፔን ውስጥ
የምታውቃት ከተማ ስም ነው:
“ለምን ግን እዚህ አመጣኸኝ?” ተሸበረች:
“ለስንብት አልሁሽ እኮ! አላት ወደ እሱ ጠጋ አድርጎ
እያቀፋት ሰውነቱ ሰውነቷን ሲነካት እየዘገነናት
“የምን ስንብት?... ደግሞ እንዴት ጨካኝ ነህ?... በአንዴ ከደስታ ወደ መከራ ትመልሰኝ..." አለችና ልሳኗ ተዘጋ: አሌክስ ሲስማት ከንፈሯ እንደ በረዶ ቀዘቀዛት።
ዙሪያቸውን እንደ እንቦቀቅላ ህፃን ድክ ድክ የሚሉት
እርግቦች አንዳች ነገር እንደመጣባቸው ሁሉ ድንገት ግር ብለው ወደ
ሃይቁ አቅጣጫ በረሩ።
አኜስ የአሌክስን እጆች ወርውራ እርግቦችን
ተመለከታቸው።
እጥፍ ብለው እንደገና ሽቅብ ጎነው በረሩ: አሌክስ ፊቷን ወደ እሱ አዙሮ
“ሰርቶ መበልፀግ ስመኘው የኖርሁትን እድል በማግኘቴ
ረክቻለሁ። ፍቅራችን ከብልፅግና ማግስት.. ጆሮዋ ደነቆረ: ከዚያ በኋላ የሚለውን አልሰማችውም።
ፍቅር ከብልፅግና
ማግስት…" አባባሉ በአእምሮዋ አስተጋባ:
ዛሬን አበላሽቶ ነገን ማስዋብ ፍቅርን ገፍትሮ ጥቅምን ማቀፍ
ተምታታባት እሪ ብለሽ ጩሂ አሰኛት… መጮህ ግን ተሳናት::ለመጮሀም ኃይል ያስፈልጋል።
አሌክስን ጠላችው 1
ገፋችው... ከዚያ እርግቦቹ ወደ ሄዱበት አቅጣጫ በረረች “አዕዋፍ ለካ ወደው ከምድር ርቀው አይበሩም ብላ በአየር ላይ ለመብረር ወደ ሰማዬ ሰማያት ለመጎን ሞከረች ትናንሽ ፍጡራን የፈፀሙትን ግን መፈፀም ተሳናት።
ይህ ከሆነና ከአሌክስ በተለየች በአምስት ዓመቷ “አሽቀንጥሬ ጣልሁት ያለችው የከንፈር ወዳጅዋ አንደገና ራባት። ፍቅሩ አገርሽቶ ጤና አሳጣት ስለዚህ ፓርቶሪኮን ለመጎብኘት በሚል ሽፋን ወደ ሳንጁአን ሄደች።
ሳን ጁአን እንደደረስችም አሌክስ በሰጣት የእርሻ ጣቢያ ማዕከል አዳራሻ ሄዳ አሌክስን እንዲያገናኝዋት ጠየቀች። በእርግጥ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ከፖርት ፕሪንስ በስተ ምስራቅ ፓርቶሪኮ ሳንጁአን ውስጥ የግል እርሻ የጀመረው አሌክስ ቀደም ሲል የስፔን ፋሽዝም
አራማጅና የጦር አባል ከነበረው ስመ ጥር አባቱ ጋር ወደ ፓርቶሪ
በተደጋጋሚ ከሄደ በኋላ ሳንጁአን ለመኖር እንዲወስን ተፈጥሮአዊ
ፍቅሩ አደፋፈረው፡
የሻምበልነት ማዕረግ የነበረው አባቱ ልጁ በእርሻ ትምህርት ሰልጥኖ ህይወቱ በእርሻ ምርት ላይ ቢመሰረት የወደፊት ዕድሉ
የተቃና ደስተኛና ሃብታም ሊሆን እንደሚችል በመከረው መሰረት
አሴክስ የአባቱን ህልም የእራሱ በማድረግ ህልሙን ለማሳካት የሚያስችለውን ጥረት ፈጽሞ በመጨረሻ ተሳካለት፡
አሌክስ ደጋግሞ ስለ እርሻ ዘመናዊ እርሻ ስለሚያስገኘው
ብልፅግና ስለ ተሻሉ የምርት ውጤቶች ማውራት እንጂ በፍቅሩ ተረትታ
እንደነፍስ ጡር ለምትብረከረከው
ፍቅረኛው ቁብ
አልነበረውም ሌላው ቀርቶ እግሩ ስር እንደምትታከከውና "ፔሙስ" ብሎ እንደሚጠራት ድመቱ ሲገናኙ እጁን ሰዶ ዳብሷት ካልያም እጆችዋን ስቦ ወደ ደረቱ አስጠግቷት አያውቅም አይብዛ እንጂ
አንድ ወቅት የፍቅር አባባሎችን ይለዋወጡ አብረውም እየተሻሹ
ጊዜያቸውን በደስታ ያሳልፉ የነበረ ቢሆንም! ያ የስሜት መመሳሰል ግን ከጠለቀ ብዙ ወራቶች ተቆጠሩ።
ይህ የቸልተኝነት ባህሪው ሸበላ ቁመናው የታከታት ደረቅ የአጨዋወት ስልቱ ሳይቀር አኜስን ለአሌክስ ያላትን ስሜት ከእለት
ወደ እለት እንዲያድግ አደረገው። አንዳንዴ እንዲያውም፡-
“አሌክስ! እባክህ ለፍቅራችን የሚሆን ጊዜ ይኑርህ? እባክህ በፍቅር
ስሜቴ አትጫወትበት!...” በማለት ምርር ብላ ስትነግረው፡-
“እባክሽ አኜስ ታገሽ!
ትዕግስት ይኑርሽ! ልትረጅኝ
ሞክሪ! በአሁኑ ሰዓት የፍቅር ስሜቴ በወደፊት ዓላማዬ እንደ ጉም ተሸፍኗል። አንድ ወቅት ግን ጉሙ ይበተናል፤ በሰማያዊው ሰማይ
ከምስራቅ ወደ ምዕራብ እንደምትጓዝ ፀሐይ የፍቅር ብርሃን ፍንትው ብሎ ይፈነጥቃል...'' ይላታል:
“አሌክስ! እኔ'ኮ ብዙ ላሳስብህ አልሻም። በሳምንት ቢያንስ
ለተወሰነ ደቂቃ እንኳ ፍቅር እንድንለዋወጥ ለማድረግ ሞክር ፧እየተጎዳሁ ነው” ስትለው፡-
“እስኪ እሞክራለሁ አንች ግን ጠንከር በይ: በህልሜ
ልትደሰች ሞክሪ በአትላንቲክ ውቅያኖስ በተከበበችው ሳን ጁን
ውስጥ የሚኖረው ቡቃያ ንፋሱ ጎንበስ ቀና ሲያደርገው ይታይሽ!
አዲዎስ ብሏት ይሄዳል።
አንድ ቀን ግን አሌክስ በጅፕ መኪናው መኖሪያዋ ድረስ መጥቶ ድንገት “ለሽርሽር እንሂድ? አላት።
“የት?” አለችው አኜስ ግራ ተጋብታ።
“ሱ..” አለ አፉን በቀኝ እጁ አመልካች ጣት እየጠበጠበ።
“አሌክስ የት እንደምንሄድ መንገሩን ባትፈልግ እንኳን ወጣ እንደምንል ቀደም ብለህ ፍንጭ መስጠት ነበረብህ: ከሰዓታት
ወይንም ከቀናት በፊት ወጣ እንደምንል ነግረኸኝ ቢሆን ኖሮ ነፍሴ በደስታ ከመዝለሏም በተጨማሪ ስሜቴ በጉጉት ተበረጋግዶ በናፍቆት ይጠብቅህ ነበር: አሁን ግን ልቤ በሐዘን ቀዝቅዛለች። ስሜቴም በድን
ነው። እኔም ስላልተዘጋጀሁ የትም መሄድ አልፈልግም” አሰችው።
ያልተለመደ ፈገግታ አሳይቶ ባልጠበቀችው መልክ የግራ እጅዋን ብድግ አድርጎ ጣቶችዋን ሳም ሳም አደረጋት፤ ጉንጯን በቀኝ
እጅ አመልካች ጣቱ ደባበሰላት: ሽቅብ አንስቶም ከንፈሯን በከንፈሩ
ደባበሰላት።
ወዲያው ልቧ ጋለች ሰውነቷ በሙቀት ተጥለቀለቀ፡
የፍቅር ሃይሏ ከየስርቻው ተሰባሰበ ስለዚህ! “ማሬ!
እንሂድ" አለችው::ሃሳቡን እንዳይለወጥ እየሰጋች: አሌክስ መኪናውን እያሽከረከረ ጭኖችዋን በቀኝ እጁ እየደባበሰ የምትሆነውን አሳጣት: ያ ጨካኙ አሌክስ ሳይሆን የፍቅር መልአክ ሆነባት…
“አሌክስ አልቻልሁም አለችው እየተስለመለመች
ጥቂት ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ።
“ትዕግስት ጥሩ ነው..."
“ኡፍ ስብከትህን አቁም። በሰዎች ሙያ ጣልቃ አትግባ መኪናዋን ይልቁንስ አቁም አለችው በትዕዛዝ መልክ፡ መኪናዋ ወደ
ዳር ወጥታ ቆመች ሞተሯ ጠፋ።
ከተቀመጠችበት ዞር ብላ እጆችዋን ዘርግታ የአሌክስን
አንገት አቀፈችው። ተገናኙ
ረሃብተኛዋ ከንፈሩን ጎረሰቸው እፅዋት በነፋሱ ጎንበስ ቀና ይላሉ ከርቤው እየጤሰ መላዕክት
እያጀቧቸው ሽቅብ በፍቅር ስረገላ አረጉ።
“አሌክስ! እኔ አላምንም... እንዴት ደስ አለኝ ለካ እንዲህ የደስታ ምንጭ ነህ እሰይ እንኳን ታገስኩህ እንኳን ቻልኩህ እንግዲህ ዳግመኛ ከፍቅር ሠረገላችን አንወርድም አይደል! ከምድር ላይ ይልቅ እዚህ ነፍስ ነህ..." እያለች ላዩ ላይ ተንከባለለችበት
የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል በርቀት ከቆሙት መርከቦችና አጠገባቸው ካለው የድንጋይ ግንብ ጋር እየተላተመ አረፋ ሲደፍቅ
ከኮሎምበስ መታሰቢያ ግዙፍ ሃውልት ትይዩ የሚነፍሰው ጤሮ ንፋስ በጆሮ ግንዷ እያፋጨ ሲያልፍ ግን አይኗን ገልጣ ከገነት ወደ ምድር ተመለሰች። ምድሯን ውቅያኖሱን ስታይ አስጠሏት፡ አሌክስ
አሁንም አብሯት አለ ያ ሲያደርጉ የነበረውና አሁን አጠገቧ ባለው አሌክስ መካከል ግን ልዩነት ያለ መሰላት፤ ተጠራጠረችው።
“ማሬ የት ነው ያለነው?" ከሰመመኗ እንደነቃች ጠየቀችው።
“ሁዌልቫ ነን! ለስንብት አመች በመሆኗ የምሄድበትንም ከርቀት ላሳይሽ ስለምችል ሁዌልቫን መርጨልሻለሁ" አላት ሳብ አድርጎ ወርቃማ ዞማ ፀጉሯን ስሞ፡
“ሁዌልቫ” ይህ ስም ምድር ላይ ያውም ስፔን ውስጥ
የምታውቃት ከተማ ስም ነው:
“ለምን ግን እዚህ አመጣኸኝ?” ተሸበረች:
“ለስንብት አልሁሽ እኮ! አላት ወደ እሱ ጠጋ አድርጎ
እያቀፋት ሰውነቱ ሰውነቷን ሲነካት እየዘገነናት
“የምን ስንብት?... ደግሞ እንዴት ጨካኝ ነህ?... በአንዴ ከደስታ ወደ መከራ ትመልሰኝ..." አለችና ልሳኗ ተዘጋ: አሌክስ ሲስማት ከንፈሯ እንደ በረዶ ቀዘቀዛት።
ዙሪያቸውን እንደ እንቦቀቅላ ህፃን ድክ ድክ የሚሉት
እርግቦች አንዳች ነገር እንደመጣባቸው ሁሉ ድንገት ግር ብለው ወደ
ሃይቁ አቅጣጫ በረሩ።
አኜስ የአሌክስን እጆች ወርውራ እርግቦችን
ተመለከታቸው።
እጥፍ ብለው እንደገና ሽቅብ ጎነው በረሩ: አሌክስ ፊቷን ወደ እሱ አዙሮ
“ሰርቶ መበልፀግ ስመኘው የኖርሁትን እድል በማግኘቴ
ረክቻለሁ። ፍቅራችን ከብልፅግና ማግስት.. ጆሮዋ ደነቆረ: ከዚያ በኋላ የሚለውን አልሰማችውም።
ፍቅር ከብልፅግና
ማግስት…" አባባሉ በአእምሮዋ አስተጋባ:
ዛሬን አበላሽቶ ነገን ማስዋብ ፍቅርን ገፍትሮ ጥቅምን ማቀፍ
ተምታታባት እሪ ብለሽ ጩሂ አሰኛት… መጮህ ግን ተሳናት::ለመጮሀም ኃይል ያስፈልጋል።
አሌክስን ጠላችው 1
ገፋችው... ከዚያ እርግቦቹ ወደ ሄዱበት አቅጣጫ በረረች “አዕዋፍ ለካ ወደው ከምድር ርቀው አይበሩም ብላ በአየር ላይ ለመብረር ወደ ሰማዬ ሰማያት ለመጎን ሞከረች ትናንሽ ፍጡራን የፈፀሙትን ግን መፈፀም ተሳናት።
ይህ ከሆነና ከአሌክስ በተለየች በአምስት ዓመቷ “አሽቀንጥሬ ጣልሁት ያለችው የከንፈር ወዳጅዋ አንደገና ራባት። ፍቅሩ አገርሽቶ ጤና አሳጣት ስለዚህ ፓርቶሪኮን ለመጎብኘት በሚል ሽፋን ወደ ሳንጁአን ሄደች።
ሳን ጁአን እንደደረስችም አሌክስ በሰጣት የእርሻ ጣቢያ ማዕከል አዳራሻ ሄዳ አሌክስን እንዲያገናኝዋት ጠየቀች። በእርግጥ
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
እራሴን አመም ስላደረገኝ አስፈቅጄ ወደቤት ስገባ ሶስት ሰዓትም አልሆነም።..ሹክክ ብዬ ገብቼ አልጋዬ ላይ "በመውጣት አረፍ እንዳልኩ ስልኬ ጠራ...አሁን ማንንም ቢሆን አንስቶ የማናገር ፍላጎት የለኝም የዜና ወርቅም ብትሆን እንኳን፡፡ስልኩ መጥራቱን ቀጥሏል ማንም ቢሆን ላለማንሳት ድምዳሜ ላይ ከደረስኩ ማንነቱንም ማየት አስፈላጊ አልነበረም ..እኔ ግን እጄን ሰድጄ ስልኬን አነሳሁ፡፡ እስክሪኑን ወደአይኔ አስጠጋሁ..ተፈናጥሬ ከመኝታዬ ተነሳሁና ቁጭ አልኩ..እንዳይዘጋብኝ እየተስገበገብኩ አነሳሁት..
‹‹ሄሎ የእኔ ውድ..?
"ሄሎ አባዬ እንዴት ነህ?
"አለሁልሽ ..በጣም ሰላም ነኝ..አልተኛሽም እንዴ?"
"አይ ገና ልተኛ እየተዘጋጀሁ ነው...አባዬ የእኔ ክላስ የትኛው እንደሆነ ታውቃለህ አይደል?"
በምናብ ወደ አደኩበት ቤት ፈረጠጥኩ..ሁሉንም ክፍሎች በሀሳቤ ቃኘሁ ከእነቴቴ መኝታ ቤት ቀጥሎ ያለችው ክፍል ነች አይደል?"ግምቴ መቼስ የቤቱ ትንሽዬ ህፃን ስለሆነች ለቁጥጥርም ለሊት ተነስቶ ደህንነቷን ለማየትም ቅርብ ያለው ክፍል ነው የሚመረጠው ብዬ ነው...፡፡
"አይደለም..እዛ ህፃን ሆኜ ነበር አሁን ትልቅ ስሆን የአንተና የእማዬ የነበረውን ክፍል ወሰድኩት
ደነገጥኩ"በእውነት እሱ ክፍል መኖሩ ትዝ አላለኝም ነበር፡፡ እንደዛ ያልኩት ከዛ ሁሉ ዝብርቅርቅ ክስተት በኃላ እቴቴ ክፍሉን ምንቅርቅር አድርጋ የአንድን ሳይድ ግድግዳ በመደርመስ ከሌላው ጋር በመቀላቀል ክፍሉ ለታሪክነትም እንዳይታወስ የምታደርገው ነበር የሚመስለኝ ..ለዛ ነው ያንን አይነት ጥያቄ የጠየቅኳት"
"ልጄ ሳይገኝ ያ ክፍል አይከፈትም ብላ ከእነዕቃው አሽጋበት ነበር...ከዛ እኔ አክስቴ ትልቋን ለመንኩና እሷ በሌለችበት አስከፈቼ ገባሁበት፡፡"
"ታዲያ አልተቆጣችሽም?"
"አይ ምንም አላለቺኝም ግን አለቀሰች፡፡"
እኔም አሁን አለቀስኩ የሚቆጠቁጥ እምባ በቀኝ ጉንጬ ረገፈ"የእኔ ማር እናትሽ ለእቴቴ ትደውልላታለች አይደል?"ድንገት በእምሮዬ ብልጭ ያልኝን ጥያቄ ጠየቅኳት፡፡
"ትደውልላታለች...እቴቴ ግን ትሰማታለች እንጂ አታናግራትም፡፡"
"ለምን?"
‹‹"እኔ እንጃ አባዬ...የሙት እህቴን ቃል እንድበላ አደረጋኛለች..ልጄን ወይ በህይወት አልያም ሞቶ ከሆነ ሬሳውን አግኝቼ እርሜን ሳላወጣ ከእሷ ጋር ባወራ እግዜር ይቀየመኛል ትላለች...ግን አባዬ እርም ማውጣት ማለት ምን ማለት ነው?።››
"ቁርጥ ማወቅ ማለት ነው የእኔ ልጅ"ቀላል ነው ብዬ ባልኩት ቃል ገለፅኩላት።
"አባዬ"
"ወዬ የእኔ ልጅ"
"እቃችሁን ስጎለጉል የእማዬ ማስታወሻ ደብተር አገኘሁት..ሁል ጊዜ አነበዋለሁ.. ደስ ይላል..።"
"እናትሽ ማስታወሻ ደብተር ነበራት እንዴ? እኔ አላውቅም..."
"አዎ አላት ..ትልቅ ሰማያዊ ደብተር....እና ደግሞ ስላንተ ብቻ ነው የፃፈችው...ትንሽ ትንሽ አንብቤው ስላልገባኝ ተውኩት.. ››
የእውነትም በጣም ተገርሜ "በእውነት ይገርማል .!"አልኩ ፡፡
በድንገት ማስታወሻው ላይ ያለውን ሀሳብ ለማወቅ የሚቀስፍ አይነት የጉጉት ስሜት ተሰማኝ..ልጄ የውስጤን እንዴት ማንበብ እንደቻለች አላውቅም"አባዬ ከፈለክ ትንሽ ትንሽ ፎቶ እያነሳው ልልክልህ እችላለሁ"ደ
ተነቃቃሁ"እንዴት አድርገሽ?"
"ቴሌግላም መጠቀም እኮ በጣም እችላለሁ...ለእማዬ ፎቶዬንና የፈተና ውጤቴን እያነሳሁ ሁሌ ነው የምልክላት"
"በጣም ደስ ይለኛል የእኔ ማር...በይ አሁን ተኚ"
"እሺ አባቢ ..ደህና እደር...እወድሀለሁ"
"እኔም እወድሻለሁ"
ስልኩ ተዘጋ...እራስ ምታት የሚባል ነገር ከጭንቅላቴ ተጠራርጎ ወዴት ጥርግ እንዳለ እኔ እንጃ።ልጅ መድሀኒት ነው የሚባለው ለካ ዝም ብሎ አባባል አይደለም፡፡
ስልኬ ተንጣጣ...ሚሴጅ ነው..ከልጄ ነው ከፈትኩት
‹‹ልኬያለሁ›› ይላል ወዲያው ዳታ አበራሁና ቴሌግራም ከፈትኩ .ተአምር እዬብ ሁለት ፋይል ልካልኛለች...የእኔ ቅመም ልጅ...፡፡ዳውን ሎድ አደረኩትና ከፈትኩት ፡፡ እውነትም ልምድ አላት ፡፡ፍይሉ በጥራት የሚነበብ በጥንቃቄ ተነስቶ የተላከ ነው።የእናቷን የእጅ ፅሁፍ ሳየው ሰውነቴን ነዘረኝ ፅሁፍና ምስሏ በአእምሮዬ እየተፈራረቀ ትዝታ ውስጥ ጨመረኝ...ምን አለ እህቴ ባትሆኚ።ትራሴን አስተካክዬ አልጋዬ ላይ ጋደም አልኩና ማንበብ ጀመርኩ።
ግንቦት 5/2008 ከምሽቱ 5 ሰዓት
እቤታችን ሲመጣ 9 አመቱ ነበር ።የመጣበትን ቀን በደንብ ነው የማስታውሰው እማዬና አባዬ ለቅሷ ብለው ወደ አዲስአባ ከሄዱ ከሳምንት በሀላ ነው ጥቁር በጥቁር ለብሰው ፊታቸው ጨልሞና ከፍቶቸው ሌላ የከፋው ፤ለንቦጩን የጣለና ግራ የገባው ልጅ ይዘው የመጡት፡፡ልጁን ቀድሞውንም አውቀዋለሁ፤ ያውቀኛል፡፡ አዲስአባ ያለችው የአክስቴ ልጅ ነው።የአሁኑ አመጣጡ ግን እንደከዚህ ቀደሙ ቦርቆና ፈንድቆ ከእኔና ከእህቶቼ ጋር ለአራት ለአምስት ቀን እቃ እቃ ተጫውቶ ለመመለስ እንዳልሆነ ገብቶኛል።
ትላልቅ ሰዎች አክስቴም ባሏም በድንገተኛ አደጋ ዘእንደሞቱ ሲያወሩ ሰምቼያለሁ ..ግን ይሄ ድንገተኛ አደጋ የተባለው ሰውን የሚገድል አውሬ ምን አይነት ነው?ስል በወቅቱ በነበረኝ የልጅነት አዕምሮዬ አሰብኩና በጣም ተበሳጨሁ። አክስቴን በተመለከተ ጣፋጭና የማይሳሳ አይነት ትዝታ ነው ያለኝ።በሶስት ወር ሆነ በስድስት ወር ልትጠይቀን ስትመጣ ..ኬክ፤ቸኮሌት፤ እና ልብስ ቀሚስ፤ ቲሸርት ጫማ ብቻ አንድ ነገር ይዛልን ትመጣ ነበር።
ትምህርት ቤት ሲዘጋ ደግሞ አዲስአባ እንሄዳለን...ያንን ቢሄድ ማለቂያ የሌለውን ከተማ በፈንጠዝያ ስንዝናናበት ቆይተን ሽክ ብለን በአዳዲስ ልብስ አሸብርቀን እንመለሳለን..አመቱን ሙሉ ከደብረብርሀን ወጥተው ለማያውቁ ጓደኞቻችን ስለአዲስአባ ተረት መሰል ታሪኮችን እየተረክን ስንጎርርባቸው እንከርማለን ለእኔ የአክስቴ ሞት ትርጉም በዛ የጨቅላነት ዕድሜዬ እንኳን በደንብ ነበር የገባኝ...ከአሁን በሀላ ከአዲስ አበባ የሚመጣልኝ ምንም ኬክ ሆነ ቸኮሌት እንደማይኖር ገባኝ..ዘናጭና ፍሽን ቀሚሶችም ከአክስቴ እንደማይበረከቱልኝ ከሁሉም በላይ ግን ክረምት መጥቶ ት/ቤት በተዘጋ ቁጥር አዲስአበባ ሄዶ መዝናናት የማይቻል መሆኑን ምን አልባትም ትልቅ ሰው እስክሆን አዲስአበባን እንደማላያት ተረዳሁ..
እና እዬቤን እማዬ ከሌሎች ሀዘንተኞች ጋር ይዛው ስትመጣ እላዩ ላይ ተጠምጥሜ አንገቱን አቅፌ አለቀስኩ..ቢያባብሉኝ እራሱ ላቆም አልቻልኩም... በወቅቱ እንደዛ ማለቀሴ አክስቴን አስታውሼ ነበር. የምታመጣልኝ ኬክና ቸኮሌትም ስላማራኝ ነበር...እናም አዲስአባም መሄድ ስለፈለኩ ግን ደግሞ እንደማልችል ስለገባኝ ነበር.፡
.ታላላቆቼ በድርጊቴ ግራ ቢጋቡም እኔ ግን በጣም አዝኜ ነበር..እና ለእዬቤ የራሱ አልጋ ከአዲስአባ እስኪመጣለት አልጋዬን አጋራሁት..እርግጥ አብዛኛውን ጊዜ እማዬ እያለ ሲቃዠና ሲንፈራገጥ እማዬ እየመጣች ወደራሷ መኝታ ቤት ትወስደውና ከማዬና አባዬ መሀል ይተኛ ነበር...እንደዛ ሲያደርግ እኔም ምን አለ አብሬው ሄጄ መሀከላቸው በተኛሁ እላለሁ፡፡እኛ ልጆቻቸው እንደው ፍርጥ እንላታለን እንጂ ከእነሱ ጋር የመተኛት እድል አናገኝም።እና በዚህ አይነት ሁኔታ እዬቤ ወንድማችን ሆነ፡፡ እቃቸው ከአዲስአባ መጣና ከእኛ ቤት እቃ ጋር ተቀላቀለ..ቤታቸውም እንደተከራየ እማዬ ስታወራ ሰምቼያለሁ። አልጋውም መጣለትና ከእኔ አልጋ ጎን ቦታ ተመቻቸለት።ግን ስንላፋና ስንጫወት ቆይተን ሳናስበው ወይ እሱ አልጋ ላይ ጥቅልል ብለን ተቃቅፈን
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////
እራሴን አመም ስላደረገኝ አስፈቅጄ ወደቤት ስገባ ሶስት ሰዓትም አልሆነም።..ሹክክ ብዬ ገብቼ አልጋዬ ላይ "በመውጣት አረፍ እንዳልኩ ስልኬ ጠራ...አሁን ማንንም ቢሆን አንስቶ የማናገር ፍላጎት የለኝም የዜና ወርቅም ብትሆን እንኳን፡፡ስልኩ መጥራቱን ቀጥሏል ማንም ቢሆን ላለማንሳት ድምዳሜ ላይ ከደረስኩ ማንነቱንም ማየት አስፈላጊ አልነበረም ..እኔ ግን እጄን ሰድጄ ስልኬን አነሳሁ፡፡ እስክሪኑን ወደአይኔ አስጠጋሁ..ተፈናጥሬ ከመኝታዬ ተነሳሁና ቁጭ አልኩ..እንዳይዘጋብኝ እየተስገበገብኩ አነሳሁት..
‹‹ሄሎ የእኔ ውድ..?
"ሄሎ አባዬ እንዴት ነህ?
"አለሁልሽ ..በጣም ሰላም ነኝ..አልተኛሽም እንዴ?"
"አይ ገና ልተኛ እየተዘጋጀሁ ነው...አባዬ የእኔ ክላስ የትኛው እንደሆነ ታውቃለህ አይደል?"
በምናብ ወደ አደኩበት ቤት ፈረጠጥኩ..ሁሉንም ክፍሎች በሀሳቤ ቃኘሁ ከእነቴቴ መኝታ ቤት ቀጥሎ ያለችው ክፍል ነች አይደል?"ግምቴ መቼስ የቤቱ ትንሽዬ ህፃን ስለሆነች ለቁጥጥርም ለሊት ተነስቶ ደህንነቷን ለማየትም ቅርብ ያለው ክፍል ነው የሚመረጠው ብዬ ነው...፡፡
"አይደለም..እዛ ህፃን ሆኜ ነበር አሁን ትልቅ ስሆን የአንተና የእማዬ የነበረውን ክፍል ወሰድኩት
ደነገጥኩ"በእውነት እሱ ክፍል መኖሩ ትዝ አላለኝም ነበር፡፡ እንደዛ ያልኩት ከዛ ሁሉ ዝብርቅርቅ ክስተት በኃላ እቴቴ ክፍሉን ምንቅርቅር አድርጋ የአንድን ሳይድ ግድግዳ በመደርመስ ከሌላው ጋር በመቀላቀል ክፍሉ ለታሪክነትም እንዳይታወስ የምታደርገው ነበር የሚመስለኝ ..ለዛ ነው ያንን አይነት ጥያቄ የጠየቅኳት"
"ልጄ ሳይገኝ ያ ክፍል አይከፈትም ብላ ከእነዕቃው አሽጋበት ነበር...ከዛ እኔ አክስቴ ትልቋን ለመንኩና እሷ በሌለችበት አስከፈቼ ገባሁበት፡፡"
"ታዲያ አልተቆጣችሽም?"
"አይ ምንም አላለቺኝም ግን አለቀሰች፡፡"
እኔም አሁን አለቀስኩ የሚቆጠቁጥ እምባ በቀኝ ጉንጬ ረገፈ"የእኔ ማር እናትሽ ለእቴቴ ትደውልላታለች አይደል?"ድንገት በእምሮዬ ብልጭ ያልኝን ጥያቄ ጠየቅኳት፡፡
"ትደውልላታለች...እቴቴ ግን ትሰማታለች እንጂ አታናግራትም፡፡"
"ለምን?"
‹‹"እኔ እንጃ አባዬ...የሙት እህቴን ቃል እንድበላ አደረጋኛለች..ልጄን ወይ በህይወት አልያም ሞቶ ከሆነ ሬሳውን አግኝቼ እርሜን ሳላወጣ ከእሷ ጋር ባወራ እግዜር ይቀየመኛል ትላለች...ግን አባዬ እርም ማውጣት ማለት ምን ማለት ነው?።››
"ቁርጥ ማወቅ ማለት ነው የእኔ ልጅ"ቀላል ነው ብዬ ባልኩት ቃል ገለፅኩላት።
"አባዬ"
"ወዬ የእኔ ልጅ"
"እቃችሁን ስጎለጉል የእማዬ ማስታወሻ ደብተር አገኘሁት..ሁል ጊዜ አነበዋለሁ.. ደስ ይላል..።"
"እናትሽ ማስታወሻ ደብተር ነበራት እንዴ? እኔ አላውቅም..."
"አዎ አላት ..ትልቅ ሰማያዊ ደብተር....እና ደግሞ ስላንተ ብቻ ነው የፃፈችው...ትንሽ ትንሽ አንብቤው ስላልገባኝ ተውኩት.. ››
የእውነትም በጣም ተገርሜ "በእውነት ይገርማል .!"አልኩ ፡፡
በድንገት ማስታወሻው ላይ ያለውን ሀሳብ ለማወቅ የሚቀስፍ አይነት የጉጉት ስሜት ተሰማኝ..ልጄ የውስጤን እንዴት ማንበብ እንደቻለች አላውቅም"አባዬ ከፈለክ ትንሽ ትንሽ ፎቶ እያነሳው ልልክልህ እችላለሁ"ደ
ተነቃቃሁ"እንዴት አድርገሽ?"
"ቴሌግላም መጠቀም እኮ በጣም እችላለሁ...ለእማዬ ፎቶዬንና የፈተና ውጤቴን እያነሳሁ ሁሌ ነው የምልክላት"
"በጣም ደስ ይለኛል የእኔ ማር...በይ አሁን ተኚ"
"እሺ አባቢ ..ደህና እደር...እወድሀለሁ"
"እኔም እወድሻለሁ"
ስልኩ ተዘጋ...እራስ ምታት የሚባል ነገር ከጭንቅላቴ ተጠራርጎ ወዴት ጥርግ እንዳለ እኔ እንጃ።ልጅ መድሀኒት ነው የሚባለው ለካ ዝም ብሎ አባባል አይደለም፡፡
ስልኬ ተንጣጣ...ሚሴጅ ነው..ከልጄ ነው ከፈትኩት
‹‹ልኬያለሁ›› ይላል ወዲያው ዳታ አበራሁና ቴሌግራም ከፈትኩ .ተአምር እዬብ ሁለት ፋይል ልካልኛለች...የእኔ ቅመም ልጅ...፡፡ዳውን ሎድ አደረኩትና ከፈትኩት ፡፡ እውነትም ልምድ አላት ፡፡ፍይሉ በጥራት የሚነበብ በጥንቃቄ ተነስቶ የተላከ ነው።የእናቷን የእጅ ፅሁፍ ሳየው ሰውነቴን ነዘረኝ ፅሁፍና ምስሏ በአእምሮዬ እየተፈራረቀ ትዝታ ውስጥ ጨመረኝ...ምን አለ እህቴ ባትሆኚ።ትራሴን አስተካክዬ አልጋዬ ላይ ጋደም አልኩና ማንበብ ጀመርኩ።
ግንቦት 5/2008 ከምሽቱ 5 ሰዓት
እቤታችን ሲመጣ 9 አመቱ ነበር ።የመጣበትን ቀን በደንብ ነው የማስታውሰው እማዬና አባዬ ለቅሷ ብለው ወደ አዲስአባ ከሄዱ ከሳምንት በሀላ ነው ጥቁር በጥቁር ለብሰው ፊታቸው ጨልሞና ከፍቶቸው ሌላ የከፋው ፤ለንቦጩን የጣለና ግራ የገባው ልጅ ይዘው የመጡት፡፡ልጁን ቀድሞውንም አውቀዋለሁ፤ ያውቀኛል፡፡ አዲስአባ ያለችው የአክስቴ ልጅ ነው።የአሁኑ አመጣጡ ግን እንደከዚህ ቀደሙ ቦርቆና ፈንድቆ ከእኔና ከእህቶቼ ጋር ለአራት ለአምስት ቀን እቃ እቃ ተጫውቶ ለመመለስ እንዳልሆነ ገብቶኛል።
ትላልቅ ሰዎች አክስቴም ባሏም በድንገተኛ አደጋ ዘእንደሞቱ ሲያወሩ ሰምቼያለሁ ..ግን ይሄ ድንገተኛ አደጋ የተባለው ሰውን የሚገድል አውሬ ምን አይነት ነው?ስል በወቅቱ በነበረኝ የልጅነት አዕምሮዬ አሰብኩና በጣም ተበሳጨሁ። አክስቴን በተመለከተ ጣፋጭና የማይሳሳ አይነት ትዝታ ነው ያለኝ።በሶስት ወር ሆነ በስድስት ወር ልትጠይቀን ስትመጣ ..ኬክ፤ቸኮሌት፤ እና ልብስ ቀሚስ፤ ቲሸርት ጫማ ብቻ አንድ ነገር ይዛልን ትመጣ ነበር።
ትምህርት ቤት ሲዘጋ ደግሞ አዲስአባ እንሄዳለን...ያንን ቢሄድ ማለቂያ የሌለውን ከተማ በፈንጠዝያ ስንዝናናበት ቆይተን ሽክ ብለን በአዳዲስ ልብስ አሸብርቀን እንመለሳለን..አመቱን ሙሉ ከደብረብርሀን ወጥተው ለማያውቁ ጓደኞቻችን ስለአዲስአባ ተረት መሰል ታሪኮችን እየተረክን ስንጎርርባቸው እንከርማለን ለእኔ የአክስቴ ሞት ትርጉም በዛ የጨቅላነት ዕድሜዬ እንኳን በደንብ ነበር የገባኝ...ከአሁን በሀላ ከአዲስ አበባ የሚመጣልኝ ምንም ኬክ ሆነ ቸኮሌት እንደማይኖር ገባኝ..ዘናጭና ፍሽን ቀሚሶችም ከአክስቴ እንደማይበረከቱልኝ ከሁሉም በላይ ግን ክረምት መጥቶ ት/ቤት በተዘጋ ቁጥር አዲስአበባ ሄዶ መዝናናት የማይቻል መሆኑን ምን አልባትም ትልቅ ሰው እስክሆን አዲስአበባን እንደማላያት ተረዳሁ..
እና እዬቤን እማዬ ከሌሎች ሀዘንተኞች ጋር ይዛው ስትመጣ እላዩ ላይ ተጠምጥሜ አንገቱን አቅፌ አለቀስኩ..ቢያባብሉኝ እራሱ ላቆም አልቻልኩም... በወቅቱ እንደዛ ማለቀሴ አክስቴን አስታውሼ ነበር. የምታመጣልኝ ኬክና ቸኮሌትም ስላማራኝ ነበር...እናም አዲስአባም መሄድ ስለፈለኩ ግን ደግሞ እንደማልችል ስለገባኝ ነበር.፡
.ታላላቆቼ በድርጊቴ ግራ ቢጋቡም እኔ ግን በጣም አዝኜ ነበር..እና ለእዬቤ የራሱ አልጋ ከአዲስአባ እስኪመጣለት አልጋዬን አጋራሁት..እርግጥ አብዛኛውን ጊዜ እማዬ እያለ ሲቃዠና ሲንፈራገጥ እማዬ እየመጣች ወደራሷ መኝታ ቤት ትወስደውና ከማዬና አባዬ መሀል ይተኛ ነበር...እንደዛ ሲያደርግ እኔም ምን አለ አብሬው ሄጄ መሀከላቸው በተኛሁ እላለሁ፡፡እኛ ልጆቻቸው እንደው ፍርጥ እንላታለን እንጂ ከእነሱ ጋር የመተኛት እድል አናገኝም።እና በዚህ አይነት ሁኔታ እዬቤ ወንድማችን ሆነ፡፡ እቃቸው ከአዲስአባ መጣና ከእኛ ቤት እቃ ጋር ተቀላቀለ..ቤታቸውም እንደተከራየ እማዬ ስታወራ ሰምቼያለሁ። አልጋውም መጣለትና ከእኔ አልጋ ጎን ቦታ ተመቻቸለት።ግን ስንላፋና ስንጫወት ቆይተን ሳናስበው ወይ እሱ አልጋ ላይ ጥቅልል ብለን ተቃቅፈን
#የዘርሲዎች_ፍቅር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አስር
ሽማግሌዎች ከዘርሲዎች አለቃ ጎጆ ፊት ለፊት ቁርበት
ተነጥፎላቸው ሲያወሩ እንደቆዩ ኮቶ ቡና የያዘ ሾርቃ አደለቻቸው"
ካርለት ጎጆው ውስጥ ሆና በቀዳዳ ታያቸዋለች ዘግይታ የወጣችው የጨረቃ ብርሃን ምሽቱን ፍንትው አድርጋ አስውባዋለች ካርለት
በልጅነቷም ሆነ በአፍላ ወጣትነቷ ብዙ ስነ ግጥሞች ስለጨረቃ
ውበት፥ ስለጨረቃ ፍቅር: ስለጨረቃ ስደት ... ተፅፈው አንብባለች
የሰለጠነው ዓለም ግን ፀሐይን እንጂ የጨረቃን ውበት ራሱ በፈበረከው የኤሌክትሪክ ብርሃን ተነጥቋል የጨረቃ ውስጠ ሚስጥር ትዝታውም ተረስቷል ሐመር ላይ ግን ጨረቃ እንደ ጥንቱ ዘመን ሙሉ አቅም: ጥንካሬ ውበት
አላት
ሽማግሎች በጨረቃ ብርሃን ምረቃ ጀመሩ፤ ምኞታቸው
ፍላጎታቸው የጋራ ነው" ሐመሮች አምላካቸውን አያስቸግሩም አንዱ ጤንነት ሌላው ንዋይ ፍቅር . ... እየተመኘ አምላኩን የሚይዘው የሚጨብጠውን
እያሳጣ ግራ አያጋባውም
ሐመሮች ዝናብና ጤንነት
ሁሌም የሚለምኑት ሁለት ነገር ነው ውስን
ብቻ ዝናብ ካለ ሳር አለ ሣር ካለ ከብቶች አሉ ከብቶች ካሉ ይኖራሉ" ሐመር ላይ ቦርጫም ምኞት የለም
የህይወት ልዩነት እንዲኖር የሚፈልግ ወይንም የሚመኝ የለም በእኩልነት እንጂ በልጦ ለመኖር የሚያስብ የለም የቤቱ ቅርፅ አንድ መልክ የቤቱ ዕቃ አንድ አለባበሱ አንድ
ሁሉም አንድ መልክ አለው ሐመር ላይ የተለዬ ያፍራል እንጂ አይኮራም፤ በመለየቱ
ይወቀሳል እንጂ አይከበርም
ሽማግሎች ቡናቸውን እንዲህ ተመራርቀው ከጠጡ በኋላ ወደ
መደነሻው ገላጣ ሜዳ ሄዱ ከተሰባሰበው የመንደሯ ሰው አቅራቢያ ተይዞ የቆመው በሬ ጂራቱን እያጠማዘዘ: ወገቡን እየለመጠ፥አንገቱን እየቀበረ ለማምለጥ ቢሞክርም ቀንድና ቀንዱን፥ ጅራቱን
የያዙት ጎረምሶች ሊያንቀሳቅሱት አልቻሉም
ሽማግሎች ከመረቁና ደልቲን የአባቱን ደንብ በማክበሩ ፕስስ እያሉ ትንፋሻቸውን ካርከፈከፉበት በኋላ የአመጣውን የቅጣት
ከብት ጉሮሮ ከወገቡ ባወጣው ጩቤ ወጋው፤ ደሙ በሾርቃ ተጠራቅሞ
የተወጋውን ከብት ጎረምሶቹ ለቀቁትና ወድቆ ተፈራገጠ ከትንሽ ጊዜ ቆይታ በኋላ ብልቱ እየወጣ ጥብሱ ተጀመረ የተዘጋጀው ከተበላ በኋላ ዳንሱ ቀጠለ ሽማግሎች ከጎረምሶችና
ልጃገረዶች ጋር ሲደንሱና ሲፎክሩ ቆይተው እኩለ ሌሊት አካባቢ
ተጠራርተው የዳንሱን ቦታ ለጎረምሶችና ልጃገረዶች ለቀው ሄዱ ልጃገረዶች በጨሌና ዛጎል የተዋበውን የፍየል ቆዳቸውን እያወናወኑ: አንባራቸውን እያፋጩ ፊታቸው ላይ የተቀቡት የአኖ ቀለም ከጨረቃዋ ብርሃን ጋር እንደ ከብቶች እያንፀባረቀ ሳቃቸው እንደ ከርሰ ምድር የእንፋሎት ውሃ ቡልቅ ፍልቅልቅ ሽቅብ ወደ ወንዶች ጆሮ እየፈሰሰ ጭፈራው ደመቀ
ጎረምሶች ረጋ ብሎ ሲፈስ የነበረውን ዳንስ ሲለውጡት
መአበሉን ሊያስነሱት ፍቅር
በጥቅማ ጥቅም የጠቦት ስብ ያልሆነበትን የፍቅር ገበያ እንዲደራ በአይነት ሰጦ ለመቀበል እንዲቻል
የቦዮን ጎዳና ሊከፍቱት
ዳንስ ሊለውጡት የወንድን ጭን ከሴት ጭን ጋር እያፏጩ የፍቅር
አረፋ ሊያስደፍቁት በማዕበሉ እየተወረወሩ
ነፍሳቸው የመጨረሻውን እርካታ ለቅፅበት ወደምታገኝበት ጫካ
ለመግባት የሚያስችላቸውን ቅላፄ ጀመሩት።
… አንች ከርታታ ከልቡ የሚያስተናግድሽ በአልኮል ፈረስ ሳይጋልብ በጥቅም
ዓይኑ ሳይታወር በምኞት ህሊናው ሳይበሰብስ
በመምሰል ቀሳፊ በሽታ ሳይጠመድ፥ በራስ መተማመኑን አኝኮ
ሳይውጥ ደስታ ሆይ! ከልቡ የሚቀበልሽ ስላለሽ ደስ ይበልሽ' እግዚኦ! በስንቱ አገር: በስንቱ ሰው ሰራሽ አበባ ለማስጌጥ በተሞከረ
ውብ ስፍራ' እየተጠራሽ ዝክር ጠይቀሽ አዝነሽ ተመለሽ! እግዚኦ!
ስንቱ በውሸት ሊያገኝሽ ተንጠራራ አንች ምስኪን ከርታታ ክብርት ደስታ ሆይ! ደስ ይበልሽ እግዚኦ! ... የሚል የመላእክት ማህሌተ
ቡራኬ በዳንሱ አካባቢ
ተሰማት ካርለት
ከርከር ከርከር ዳሌ ወዝወዝ ወገብና አንገት ሰበቅ
ሰበቅ ... እጥፍ እጥፍ፥ ዘርጋ ዘርጋ ዳሌ ወዝወዝ: ሣቅ ሣቅ ሆኖ አሀሀ-ሎሜ!
መባል ተጀመረ ተሟሟቀ የወንዶችና የልጃገረዶች
ሰውነት ልጃገረዶች የሚፈልጉትን ወንድ
እየተወረወሩ እየሄዱ ጋብዘው ወዲያ ወዲህ ሽርር ሽርር … እያሉ
ሲጠብቁ የተመረጡት ወንዶች ወገብ ለወገብ ከጓደኞቻቸው ጋር
ከተያያዙበት እየተላቀቁ እንደ ጎራዴ ምዝዝ: መሬቷን ድልቅ፥ ሸብሸብ ደሞ ዝልል
እያሉ ወደ ጋባዦቻቸው ተጠጉና ወገብ ለወገብ እየተያያዙ ገቡ ባልጩቱ
ተጠልፎ እንደ ኤሌክትሪክ ገመድ ጫፍ ተገናኘ ሞገዱ ተለቀቀ የጡት ጫፍ ሊወርድ እንደተቃረበ ጀት ጎማ ከተጣጠፈበት እየተዘረጋጋ ቆመ ተሳሳለ ቢላዋና ሞረዱ ስለቱ የፍቅር ጮማውን ቆርጦ ወደ የአፋቸው አስጠጋው አላመጡት: አደቀቁት አልመው ዋጡት ያን ምርጥ የሐመር ሰንጋ የፍቅር ጮማ ልብ ቦታውን
እየለቀቀች ዘለለች ህሊና ትዕዛዝ ሰጠ ደስታ ሆይ አንቺ ከርታታ ምስኪን ሆይ ደስ ይበልሽ! ማህሌቱ አላቆመም ካርለት
ይህን ሰማያዊና ምድራዊ የተጣጣመ ትርዒት ፈዛ ስትመለከት ለረጅም ጊዜ ቆየች ኮቶ ከኋላዋ መጥታ ባትነካትማ የምትነቃ
አትመስልም ቅዠት የሌለበት ህልም ... ፍርሃት የሌለበት ደስታ።
"ኮቶ ልትደንሽ ወደ ዳንሱ ገብተሽ ከኋላዬ የምትመጭው ከየት
ነው?" አለቻት ካርለት ዐይን ዐይኖችዋን እያየች
"ይእ! ጥጆችን ሳራክብ እሁ አለፉኝ ሲራከቡ!" ብላ
የካርለትን ትከሻ ተደገፈች "ነው!" ካርለት ገባት የቆየችበት የኮቶ ሰውነት ዛል ብሏል ሰውነቷ እንደ እንቦሳ ሰውነት ያረግዳል
የእርካታ ትንፋሽዋ በመላ ሰውነቷ ይትጎለጎላል
"ኮቶ ደልቲን ልጋብዘው?"
"ይእ! ኧረ ተይ ከእጮኛ ጋርማ አይደነስም እሱ ከፈለገ መጥቶ ሲጠራሽ ባይሆን አጠገቡ ትሄጃለሽ ከዚያ እያወጋችሁ ቀስ
በቀስ ከዳንሱ ቦታ ፈንጠር፥ ፈንጠር ... እያላችሁ በመጨረሻ ጨረቃዋን እፍ' ብላችሁ አሹፋችሁባት ትጠፋላችሁ እሷም ቀልድ
ስለምትወድ እየሳቀች ትከተላችኋለች ካለ ጨረቃ የወንድና ልጃገረድን ፍቅር ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ የሚያውቀው
የለም!"
"የመንደራችን ጎረምሶች ግን ተእንግዲህ ትቀመስ ማለታቸው አይቀርም የአባትሽ ዘመዶች (እንደናሶችም) እንደ እኛ ይገርፉሻል"በይ እቴ ወሬው ይብቃ እንጫወት" ብላ በቆሙበት መወዛወዝ
ጀመሩ"
ደልቲ ከዳንሱ ወጥቶ ካርለት አባት ብላ የመረጠችውን ዘመድ
ረምሳ ጠራውና በርኮታው ላይ ተቀመጠ" ጎረምሳው
ጥሪውን ተቀብሎ አጠገቡ ሄዶ ቁጭ አለ
"ሚሶ!" አለው ደልቲ
"ሚሶ!" አለ ጎረምሳው"
"...ይህችን ልጅ የአባት ወጓን አስተምሯት እንጂ?"
"እእ! - ካርለቴን ነው?"
"አዎ! ከብትና ፍዬል ትጠብቅ ቀፎም ትስቀል ዳንሱ ላይም ግረፏት እንጂ. አሁን ታልሰባች በኋላ እኔ ስንቱን ላርማት ነው?"
"እእ! እሽ ኧረ እኛም ስንመክርበት ነበር እንዳልኸውስ ተሌሎች እህቶቻችን ነጥለን ለምን እናያታለን! ትንሽ
እሚያሰቃጥጠው እንኳን ተገርፋ ሌሎቹ ሲገረፉ ስታይ ንዳድ
እንደያዘው ሰው እየተንቀጠቀጠች መግቢያው ነው የሚጠፋት,,
"አይቻታለሁ ባትለምደው ነው! ግዴለም አስለምዷት
ተዚያ እሷው ያምራታል እሷ እኮ ህፃን ማለት ናት ህፃንን
ብትመታው ያለቅሳል
ሴቷ ግን እድሜ ለአባቷ
ለመንደሯ ጎረምሶች እያደገች ስትሄድ እያየች ትማርና በኋላ በተግባር ደሞ ቀስ በቀስ ትለምዳለች, ትፈራለች ብላችሁ አትተዋት
የኖረችበትን መገመቱ ይከብዳል! እነሱ በድለዋታልና እኛም ግን
ደግመን ልንበድላት አይገባም የዱላን ፍቅር አሳይዋት እሷም ተተወሰነ ጊዜ በኋላ ፍርሃቱ ይወጣላታል!"
"እእ!- እሽ ዛሬስ እኛም አስበናታል ና እንጂ አንተስ
ተጫዋት?"
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
፡
፡
#ክፍል_አስር
ሽማግሌዎች ከዘርሲዎች አለቃ ጎጆ ፊት ለፊት ቁርበት
ተነጥፎላቸው ሲያወሩ እንደቆዩ ኮቶ ቡና የያዘ ሾርቃ አደለቻቸው"
ካርለት ጎጆው ውስጥ ሆና በቀዳዳ ታያቸዋለች ዘግይታ የወጣችው የጨረቃ ብርሃን ምሽቱን ፍንትው አድርጋ አስውባዋለች ካርለት
በልጅነቷም ሆነ በአፍላ ወጣትነቷ ብዙ ስነ ግጥሞች ስለጨረቃ
ውበት፥ ስለጨረቃ ፍቅር: ስለጨረቃ ስደት ... ተፅፈው አንብባለች
የሰለጠነው ዓለም ግን ፀሐይን እንጂ የጨረቃን ውበት ራሱ በፈበረከው የኤሌክትሪክ ብርሃን ተነጥቋል የጨረቃ ውስጠ ሚስጥር ትዝታውም ተረስቷል ሐመር ላይ ግን ጨረቃ እንደ ጥንቱ ዘመን ሙሉ አቅም: ጥንካሬ ውበት
አላት
ሽማግሎች በጨረቃ ብርሃን ምረቃ ጀመሩ፤ ምኞታቸው
ፍላጎታቸው የጋራ ነው" ሐመሮች አምላካቸውን አያስቸግሩም አንዱ ጤንነት ሌላው ንዋይ ፍቅር . ... እየተመኘ አምላኩን የሚይዘው የሚጨብጠውን
እያሳጣ ግራ አያጋባውም
ሐመሮች ዝናብና ጤንነት
ሁሌም የሚለምኑት ሁለት ነገር ነው ውስን
ብቻ ዝናብ ካለ ሳር አለ ሣር ካለ ከብቶች አሉ ከብቶች ካሉ ይኖራሉ" ሐመር ላይ ቦርጫም ምኞት የለም
የህይወት ልዩነት እንዲኖር የሚፈልግ ወይንም የሚመኝ የለም በእኩልነት እንጂ በልጦ ለመኖር የሚያስብ የለም የቤቱ ቅርፅ አንድ መልክ የቤቱ ዕቃ አንድ አለባበሱ አንድ
ሁሉም አንድ መልክ አለው ሐመር ላይ የተለዬ ያፍራል እንጂ አይኮራም፤ በመለየቱ
ይወቀሳል እንጂ አይከበርም
ሽማግሎች ቡናቸውን እንዲህ ተመራርቀው ከጠጡ በኋላ ወደ
መደነሻው ገላጣ ሜዳ ሄዱ ከተሰባሰበው የመንደሯ ሰው አቅራቢያ ተይዞ የቆመው በሬ ጂራቱን እያጠማዘዘ: ወገቡን እየለመጠ፥አንገቱን እየቀበረ ለማምለጥ ቢሞክርም ቀንድና ቀንዱን፥ ጅራቱን
የያዙት ጎረምሶች ሊያንቀሳቅሱት አልቻሉም
ሽማግሎች ከመረቁና ደልቲን የአባቱን ደንብ በማክበሩ ፕስስ እያሉ ትንፋሻቸውን ካርከፈከፉበት በኋላ የአመጣውን የቅጣት
ከብት ጉሮሮ ከወገቡ ባወጣው ጩቤ ወጋው፤ ደሙ በሾርቃ ተጠራቅሞ
የተወጋውን ከብት ጎረምሶቹ ለቀቁትና ወድቆ ተፈራገጠ ከትንሽ ጊዜ ቆይታ በኋላ ብልቱ እየወጣ ጥብሱ ተጀመረ የተዘጋጀው ከተበላ በኋላ ዳንሱ ቀጠለ ሽማግሎች ከጎረምሶችና
ልጃገረዶች ጋር ሲደንሱና ሲፎክሩ ቆይተው እኩለ ሌሊት አካባቢ
ተጠራርተው የዳንሱን ቦታ ለጎረምሶችና ልጃገረዶች ለቀው ሄዱ ልጃገረዶች በጨሌና ዛጎል የተዋበውን የፍየል ቆዳቸውን እያወናወኑ: አንባራቸውን እያፋጩ ፊታቸው ላይ የተቀቡት የአኖ ቀለም ከጨረቃዋ ብርሃን ጋር እንደ ከብቶች እያንፀባረቀ ሳቃቸው እንደ ከርሰ ምድር የእንፋሎት ውሃ ቡልቅ ፍልቅልቅ ሽቅብ ወደ ወንዶች ጆሮ እየፈሰሰ ጭፈራው ደመቀ
ጎረምሶች ረጋ ብሎ ሲፈስ የነበረውን ዳንስ ሲለውጡት
መአበሉን ሊያስነሱት ፍቅር
በጥቅማ ጥቅም የጠቦት ስብ ያልሆነበትን የፍቅር ገበያ እንዲደራ በአይነት ሰጦ ለመቀበል እንዲቻል
የቦዮን ጎዳና ሊከፍቱት
ዳንስ ሊለውጡት የወንድን ጭን ከሴት ጭን ጋር እያፏጩ የፍቅር
አረፋ ሊያስደፍቁት በማዕበሉ እየተወረወሩ
ነፍሳቸው የመጨረሻውን እርካታ ለቅፅበት ወደምታገኝበት ጫካ
ለመግባት የሚያስችላቸውን ቅላፄ ጀመሩት።
… አንች ከርታታ ከልቡ የሚያስተናግድሽ በአልኮል ፈረስ ሳይጋልብ በጥቅም
ዓይኑ ሳይታወር በምኞት ህሊናው ሳይበሰብስ
በመምሰል ቀሳፊ በሽታ ሳይጠመድ፥ በራስ መተማመኑን አኝኮ
ሳይውጥ ደስታ ሆይ! ከልቡ የሚቀበልሽ ስላለሽ ደስ ይበልሽ' እግዚኦ! በስንቱ አገር: በስንቱ ሰው ሰራሽ አበባ ለማስጌጥ በተሞከረ
ውብ ስፍራ' እየተጠራሽ ዝክር ጠይቀሽ አዝነሽ ተመለሽ! እግዚኦ!
ስንቱ በውሸት ሊያገኝሽ ተንጠራራ አንች ምስኪን ከርታታ ክብርት ደስታ ሆይ! ደስ ይበልሽ እግዚኦ! ... የሚል የመላእክት ማህሌተ
ቡራኬ በዳንሱ አካባቢ
ተሰማት ካርለት
ከርከር ከርከር ዳሌ ወዝወዝ ወገብና አንገት ሰበቅ
ሰበቅ ... እጥፍ እጥፍ፥ ዘርጋ ዘርጋ ዳሌ ወዝወዝ: ሣቅ ሣቅ ሆኖ አሀሀ-ሎሜ!
መባል ተጀመረ ተሟሟቀ የወንዶችና የልጃገረዶች
ሰውነት ልጃገረዶች የሚፈልጉትን ወንድ
እየተወረወሩ እየሄዱ ጋብዘው ወዲያ ወዲህ ሽርር ሽርር … እያሉ
ሲጠብቁ የተመረጡት ወንዶች ወገብ ለወገብ ከጓደኞቻቸው ጋር
ከተያያዙበት እየተላቀቁ እንደ ጎራዴ ምዝዝ: መሬቷን ድልቅ፥ ሸብሸብ ደሞ ዝልል
እያሉ ወደ ጋባዦቻቸው ተጠጉና ወገብ ለወገብ እየተያያዙ ገቡ ባልጩቱ
ተጠልፎ እንደ ኤሌክትሪክ ገመድ ጫፍ ተገናኘ ሞገዱ ተለቀቀ የጡት ጫፍ ሊወርድ እንደተቃረበ ጀት ጎማ ከተጣጠፈበት እየተዘረጋጋ ቆመ ተሳሳለ ቢላዋና ሞረዱ ስለቱ የፍቅር ጮማውን ቆርጦ ወደ የአፋቸው አስጠጋው አላመጡት: አደቀቁት አልመው ዋጡት ያን ምርጥ የሐመር ሰንጋ የፍቅር ጮማ ልብ ቦታውን
እየለቀቀች ዘለለች ህሊና ትዕዛዝ ሰጠ ደስታ ሆይ አንቺ ከርታታ ምስኪን ሆይ ደስ ይበልሽ! ማህሌቱ አላቆመም ካርለት
ይህን ሰማያዊና ምድራዊ የተጣጣመ ትርዒት ፈዛ ስትመለከት ለረጅም ጊዜ ቆየች ኮቶ ከኋላዋ መጥታ ባትነካትማ የምትነቃ
አትመስልም ቅዠት የሌለበት ህልም ... ፍርሃት የሌለበት ደስታ።
"ኮቶ ልትደንሽ ወደ ዳንሱ ገብተሽ ከኋላዬ የምትመጭው ከየት
ነው?" አለቻት ካርለት ዐይን ዐይኖችዋን እያየች
"ይእ! ጥጆችን ሳራክብ እሁ አለፉኝ ሲራከቡ!" ብላ
የካርለትን ትከሻ ተደገፈች "ነው!" ካርለት ገባት የቆየችበት የኮቶ ሰውነት ዛል ብሏል ሰውነቷ እንደ እንቦሳ ሰውነት ያረግዳል
የእርካታ ትንፋሽዋ በመላ ሰውነቷ ይትጎለጎላል
"ኮቶ ደልቲን ልጋብዘው?"
"ይእ! ኧረ ተይ ከእጮኛ ጋርማ አይደነስም እሱ ከፈለገ መጥቶ ሲጠራሽ ባይሆን አጠገቡ ትሄጃለሽ ከዚያ እያወጋችሁ ቀስ
በቀስ ከዳንሱ ቦታ ፈንጠር፥ ፈንጠር ... እያላችሁ በመጨረሻ ጨረቃዋን እፍ' ብላችሁ አሹፋችሁባት ትጠፋላችሁ እሷም ቀልድ
ስለምትወድ እየሳቀች ትከተላችኋለች ካለ ጨረቃ የወንድና ልጃገረድን ፍቅር ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ የሚያውቀው
የለም!"
"የመንደራችን ጎረምሶች ግን ተእንግዲህ ትቀመስ ማለታቸው አይቀርም የአባትሽ ዘመዶች (እንደናሶችም) እንደ እኛ ይገርፉሻል"በይ እቴ ወሬው ይብቃ እንጫወት" ብላ በቆሙበት መወዛወዝ
ጀመሩ"
ደልቲ ከዳንሱ ወጥቶ ካርለት አባት ብላ የመረጠችውን ዘመድ
ረምሳ ጠራውና በርኮታው ላይ ተቀመጠ" ጎረምሳው
ጥሪውን ተቀብሎ አጠገቡ ሄዶ ቁጭ አለ
"ሚሶ!" አለው ደልቲ
"ሚሶ!" አለ ጎረምሳው"
"...ይህችን ልጅ የአባት ወጓን አስተምሯት እንጂ?"
"እእ! - ካርለቴን ነው?"
"አዎ! ከብትና ፍዬል ትጠብቅ ቀፎም ትስቀል ዳንሱ ላይም ግረፏት እንጂ. አሁን ታልሰባች በኋላ እኔ ስንቱን ላርማት ነው?"
"እእ! እሽ ኧረ እኛም ስንመክርበት ነበር እንዳልኸውስ ተሌሎች እህቶቻችን ነጥለን ለምን እናያታለን! ትንሽ
እሚያሰቃጥጠው እንኳን ተገርፋ ሌሎቹ ሲገረፉ ስታይ ንዳድ
እንደያዘው ሰው እየተንቀጠቀጠች መግቢያው ነው የሚጠፋት,,
"አይቻታለሁ ባትለምደው ነው! ግዴለም አስለምዷት
ተዚያ እሷው ያምራታል እሷ እኮ ህፃን ማለት ናት ህፃንን
ብትመታው ያለቅሳል
ሴቷ ግን እድሜ ለአባቷ
ለመንደሯ ጎረምሶች እያደገች ስትሄድ እያየች ትማርና በኋላ በተግባር ደሞ ቀስ በቀስ ትለምዳለች, ትፈራለች ብላችሁ አትተዋት
የኖረችበትን መገመቱ ይከብዳል! እነሱ በድለዋታልና እኛም ግን
ደግመን ልንበድላት አይገባም የዱላን ፍቅር አሳይዋት እሷም ተተወሰነ ጊዜ በኋላ ፍርሃቱ ይወጣላታል!"
"እእ!- እሽ ዛሬስ እኛም አስበናታል ና እንጂ አንተስ
ተጫዋት?"
#ባል_አስይዞ_ቁማር
:
:
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹ካልደበረሽ እኔ አንድ ቦታ ልውሰድሽ፡፡›› አላት…
ደስ አላት ፡፡ምክንያቱም የሆነ ውብ ስፍራ ለመጀመሪያ ጊዜ ይዟት እንደሚሄድ ገመተች..ያ ማለት ደግሞ አንድ ከእሱ ጋር የሚያቆራኛትን ትዝታ በልብ የማስቀመጠ አጋጣሚ ተፈጠረላት ማለት ነው፡፡አንደዛ ስላሰበች ነው በጣም የተደሰተችው፡
‹‹በጣም ደስ ይለኛል….በል ተነስ እንሂድ…››ብድግ አለች.፡፤
ቆይ ጃኬት ልልበስ አለና ወደ መኝታ ቤቱ ገብቶ ጃኬቱን ለብሶ በአንድ እጁ ብሮች ይዞ መጣና አቀበላት፡፡
‹‹ምንድነው?››ግራ ገብቷት ጠየቀችው፡፡
‹‹ያዢው ዛሬ ጋባዥ አንቺ ነሽ..››አላት፡፡
ለሊት በዛ ንዴት የመለስችለትን ብር በዘዴና በጨዋ ደንብ መመለሱ እንደሆነ ገባት፡፡
‹‹ሌላ ብዙ ብር ይዤያለሁ እኮ..››
‹‹አሪፍ ነዋ..ብዙ እንዝናናበታለን››አላት፡፡
‹‹የማንኛውም ጥያቄ መልስ ከንፈሩ ላይ ነው፡››አለ..በውስጧ፡፡
ብዙም ክርክር ውስጥ መግባት ስላልፈለገች… ብሩን ቦርሳዋ ውስጥ ከተተች‹‹ አንዴ መኝታ ቤትህን ልጠቀም ሜካፔን ላስተካክል.. መስታወት እዛ ያለ መሰለኝ፡፡››
‹‹ይቻላል ተጠቀሚ ..ቁም ሳጥኑ ላይ አለልሽ››አላት…፡፡
‹‹እሺ ብላ ቦርሳዋን አንጠልጥላ ወደመኝታ ቤቱ ገባችና ከውስጥ ዘጋችው፡፡
ሜካፔን ለማስተካከል ፍፅም ሀሳብ የላትም….መኝታ ቤቱ የገባችው ለሌላ ቀሺም ስራ ነው…እንደለመደችው ልትሰርቅ አይደለም…ግን ደግሞ ያው ስርቆት በሉት፡፡ ቦርሳዋን በረበርችና ብይ የምታህል ዘመናዊ የመቅረጫ መሳሪያ አወጣች…እንደዚህ አይነት ዘመናዊ የመቅረጫ መሳሪያዎች በጣም ብዙ አላት..የእሷን ያህል የሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤትም ያለው አይመስልም…የዛሬ አመት አሜሪካ የሄደች ጊዜ ነው በአጋጣሚ እጇ የገባውና ከጌጣጌጦቸና ኮስሞቲኮቾ ጋር ቀላቅላ ወደሀገር ይዛ የገባችው….
እና ስለሆነ ሰው የሆነ ነገር የማወቅ ጥማት እረፍት ሲነሳት ትጠቀምባቸዋለች፡፡መኝታ ቤቱን በአይኗ ቃኘችና ቦታ ፈለገች፡፡ ከእሱ የምርቃቱ ፎቶ ፍሬም ላይ ልታስቀምጠው ፈለገችና ወዲያው ሀሳቧን ቀየረች፡፡እሱ ልጅ ሆኖ በእናቱና በአባቱ መካከል ቆሞ የተነሳውን ፎቶ መረጠች..ወደአዛ ቀረበችና በጥንቃቄ አስቀመጠችው፡፡ ከቦርሳዋ ለእንደዚህ አይነት ጉዳይ የምትጠቀምበትን ማጣበቂያ አውጥታ እንዳይንቀሳቀስ አድርጋ አጣበቀችው… ሞባይሏን አወጣችውና ከፈተችው ..ጢው ጡው እያለ መአት ሚሴጅ እየተግተለተለ ገባላት፡፡ ችላ አለችና ከካሜራው ጋር ሚያገናኘውን አፕ አበራችውና መቆጣጠሪያ ቁልፉን በመክፈት አገናኘችው፡፡ ከዛ በትክክል መስራቱን አረጋገጠች፡፡
አዎ ከሞላ ጎደል ከዚህቺ ሰዓት አንስቶ እዚህ ክፍል ውስጥ የሚከናወነውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ሆነ ንግግር እቤቷ ሆነ ሌላ በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ባለ በማንኛውም ቦታ ሆና መከታተል ትችላለች…..ይሄም አንዱ መጥፎ ጎኗ ነው…ያው ሌብነት በሉት….
የሰውን የግል ህይወት ያለፍቃዱ ጠልፎ ማዳመጥና መቅዳት ስርቆት ካልተባለ ሌላ ምን ይባላል? እንደውም ከስርቆትም ጠንከር ያለ ወንጀል ነው….፡፡
በዛን ደቂቃ ግን ቃል ኪስ ውስጥ ያለው ሞባይል ቅጭልጭልታ ድምፅ አሰማ…ግራ ገባው.. አውጥቶ አየው…በጣም ተገረመ..ምን እየተፈጠረ ነው….?እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ?›እራሱን በሚገርም ጥያቄ አጨናነቀ፡፡
ሁሉን ነገር አጠናቅቃ ስትወጣ ቀልም ምንም እንዳልተፈጠረ በማስመሰል የፊትለፊቱ በራፍ ጋር ቆሞ ሲጠብቀት ነበር፡፡እቤቱን ለቆ ወጣ ፡፡ተከተለችው፡፡ በራፉን ቆለፈና ወጡ.. ቀጥታ ወደበሩ ስያመራ የውጩን በራፍ ሊከፍትላት መስሏት ነበር፡፡ እሱ ግን ትንሿን በራፍ ከፈተና ወደኃላ ዞረ…‹‹ምነው ቆምሽ …አትመጪም እንዴ?››አላት፡፡
‹‹በራፍን ክፈትልኝ እንጂ መኪናዬን ላስወጣ..፡፡››
‹‹መኪናዋ ያንቺ ነች እንዴ… ?እማማ ጋር የመጣ እንግዳ መስሎኝ ነበር እኮ›› አለና ትልቁን በራፍ ለመክፈት መታገል ጀመረ…እሷም ወደመኪናዋ ገባችና ሞተሩ አስነሳች…መኪና ይዛ እስከ ግቢው መምጣቷ ያልጠበቀው እንደሆነ ቢያስታውቅበትም የገመተችውን ያህል ግን መደነቅ አላየችበትም
‹‹…ሌላ ወንድ ቢሆን በአድናቆት አፍን ከፍቶ ለሀጪን ያዝረከርክ ነበር..ይሄ እንደው ሲሞቅም ሲቀዘቅዝ አንድ ጌጅ ያህል ብቻ ነው ከፍ ዝቅ የሚለው….ሰው እንዴት በዚህ ልክ ስሜቱን መግራት ይችላል?፡፡››ስትል አጉተመተመች፡፡
በራፉን ከፍቶ ሲጨርስ መኪናዋን አንቀሰቀስችና ከግቢው እስወጣቻት..እሱም የከፈተውን በራፍ መልሶ ዘግቶ ሄዶ ተቀላቀላት፡፡
‹‹ ወደየት ልንዳው?››ጠየቀችው፡፡
‹‹ወደሜቅዶኒያ››
‹‹እርግጠኛ ነህ››ያልጠበቀችውን ስም ስለጠራላት ግራ ተጋባች..እሷ እንጦጦ ወይ አንድነት፤ካልሆም እስካይ ላይት እንደው ካነሰ ካነስ የሆነ ሲኒማ ወይም ቲያትር ቤት አንሂድ ይለኛል ብላ ነበር የጠበቀችው፡፡
..እንሂድ ወዳላት ቦታ ለመሄድ ብዙም ደስተኛ እንዳልሆነች በመገመት‹‹አዎ ምነው…?አባቴ እዛ ነው የሚኖረው ..በየሳምንቱ በዚህን ሰአት ይጠብቀኛል..ባይሆን ከዛ መልስ አንቺ የፈለግሽው ቦታ እንሄዳለን፡፡›አላት፡፡
‹‹አረ ችግር የለውም..እንዲሁ ያልጠበቅኩት ቦታ ስለሆነ ነው››ብላ በምትሄድበት ቦታ እንዳልተከፋች ተናገረች…እውነታው ግን እንደዛ አልነበረም፡፡
✨ይቀጥላል✨
:
:
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
‹‹ካልደበረሽ እኔ አንድ ቦታ ልውሰድሽ፡፡›› አላት…
ደስ አላት ፡፡ምክንያቱም የሆነ ውብ ስፍራ ለመጀመሪያ ጊዜ ይዟት እንደሚሄድ ገመተች..ያ ማለት ደግሞ አንድ ከእሱ ጋር የሚያቆራኛትን ትዝታ በልብ የማስቀመጠ አጋጣሚ ተፈጠረላት ማለት ነው፡፡አንደዛ ስላሰበች ነው በጣም የተደሰተችው፡
‹‹በጣም ደስ ይለኛል….በል ተነስ እንሂድ…››ብድግ አለች.፡፤
ቆይ ጃኬት ልልበስ አለና ወደ መኝታ ቤቱ ገብቶ ጃኬቱን ለብሶ በአንድ እጁ ብሮች ይዞ መጣና አቀበላት፡፡
‹‹ምንድነው?››ግራ ገብቷት ጠየቀችው፡፡
‹‹ያዢው ዛሬ ጋባዥ አንቺ ነሽ..››አላት፡፡
ለሊት በዛ ንዴት የመለስችለትን ብር በዘዴና በጨዋ ደንብ መመለሱ እንደሆነ ገባት፡፡
‹‹ሌላ ብዙ ብር ይዤያለሁ እኮ..››
‹‹አሪፍ ነዋ..ብዙ እንዝናናበታለን››አላት፡፡
‹‹የማንኛውም ጥያቄ መልስ ከንፈሩ ላይ ነው፡››አለ..በውስጧ፡፡
ብዙም ክርክር ውስጥ መግባት ስላልፈለገች… ብሩን ቦርሳዋ ውስጥ ከተተች‹‹ አንዴ መኝታ ቤትህን ልጠቀም ሜካፔን ላስተካክል.. መስታወት እዛ ያለ መሰለኝ፡፡››
‹‹ይቻላል ተጠቀሚ ..ቁም ሳጥኑ ላይ አለልሽ››አላት…፡፡
‹‹እሺ ብላ ቦርሳዋን አንጠልጥላ ወደመኝታ ቤቱ ገባችና ከውስጥ ዘጋችው፡፡
ሜካፔን ለማስተካከል ፍፅም ሀሳብ የላትም….መኝታ ቤቱ የገባችው ለሌላ ቀሺም ስራ ነው…እንደለመደችው ልትሰርቅ አይደለም…ግን ደግሞ ያው ስርቆት በሉት፡፡ ቦርሳዋን በረበርችና ብይ የምታህል ዘመናዊ የመቅረጫ መሳሪያ አወጣች…እንደዚህ አይነት ዘመናዊ የመቅረጫ መሳሪያዎች በጣም ብዙ አላት..የእሷን ያህል የሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤትም ያለው አይመስልም…የዛሬ አመት አሜሪካ የሄደች ጊዜ ነው በአጋጣሚ እጇ የገባውና ከጌጣጌጦቸና ኮስሞቲኮቾ ጋር ቀላቅላ ወደሀገር ይዛ የገባችው….
እና ስለሆነ ሰው የሆነ ነገር የማወቅ ጥማት እረፍት ሲነሳት ትጠቀምባቸዋለች፡፡መኝታ ቤቱን በአይኗ ቃኘችና ቦታ ፈለገች፡፡ ከእሱ የምርቃቱ ፎቶ ፍሬም ላይ ልታስቀምጠው ፈለገችና ወዲያው ሀሳቧን ቀየረች፡፡እሱ ልጅ ሆኖ በእናቱና በአባቱ መካከል ቆሞ የተነሳውን ፎቶ መረጠች..ወደአዛ ቀረበችና በጥንቃቄ አስቀመጠችው፡፡ ከቦርሳዋ ለእንደዚህ አይነት ጉዳይ የምትጠቀምበትን ማጣበቂያ አውጥታ እንዳይንቀሳቀስ አድርጋ አጣበቀችው… ሞባይሏን አወጣችውና ከፈተችው ..ጢው ጡው እያለ መአት ሚሴጅ እየተግተለተለ ገባላት፡፡ ችላ አለችና ከካሜራው ጋር ሚያገናኘውን አፕ አበራችውና መቆጣጠሪያ ቁልፉን በመክፈት አገናኘችው፡፡ ከዛ በትክክል መስራቱን አረጋገጠች፡፡
አዎ ከሞላ ጎደል ከዚህቺ ሰዓት አንስቶ እዚህ ክፍል ውስጥ የሚከናወነውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ ሆነ ንግግር እቤቷ ሆነ ሌላ በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ባለ በማንኛውም ቦታ ሆና መከታተል ትችላለች…..ይሄም አንዱ መጥፎ ጎኗ ነው…ያው ሌብነት በሉት….
የሰውን የግል ህይወት ያለፍቃዱ ጠልፎ ማዳመጥና መቅዳት ስርቆት ካልተባለ ሌላ ምን ይባላል? እንደውም ከስርቆትም ጠንከር ያለ ወንጀል ነው….፡፡
በዛን ደቂቃ ግን ቃል ኪስ ውስጥ ያለው ሞባይል ቅጭልጭልታ ድምፅ አሰማ…ግራ ገባው.. አውጥቶ አየው…በጣም ተገረመ..ምን እየተፈጠረ ነው….?እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ?›እራሱን በሚገርም ጥያቄ አጨናነቀ፡፡
ሁሉን ነገር አጠናቅቃ ስትወጣ ቀልም ምንም እንዳልተፈጠረ በማስመሰል የፊትለፊቱ በራፍ ጋር ቆሞ ሲጠብቀት ነበር፡፡እቤቱን ለቆ ወጣ ፡፡ተከተለችው፡፡ በራፉን ቆለፈና ወጡ.. ቀጥታ ወደበሩ ስያመራ የውጩን በራፍ ሊከፍትላት መስሏት ነበር፡፡ እሱ ግን ትንሿን በራፍ ከፈተና ወደኃላ ዞረ…‹‹ምነው ቆምሽ …አትመጪም እንዴ?››አላት፡፡
‹‹በራፍን ክፈትልኝ እንጂ መኪናዬን ላስወጣ..፡፡››
‹‹መኪናዋ ያንቺ ነች እንዴ… ?እማማ ጋር የመጣ እንግዳ መስሎኝ ነበር እኮ›› አለና ትልቁን በራፍ ለመክፈት መታገል ጀመረ…እሷም ወደመኪናዋ ገባችና ሞተሩ አስነሳች…መኪና ይዛ እስከ ግቢው መምጣቷ ያልጠበቀው እንደሆነ ቢያስታውቅበትም የገመተችውን ያህል ግን መደነቅ አላየችበትም
‹‹…ሌላ ወንድ ቢሆን በአድናቆት አፍን ከፍቶ ለሀጪን ያዝረከርክ ነበር..ይሄ እንደው ሲሞቅም ሲቀዘቅዝ አንድ ጌጅ ያህል ብቻ ነው ከፍ ዝቅ የሚለው….ሰው እንዴት በዚህ ልክ ስሜቱን መግራት ይችላል?፡፡››ስትል አጉተመተመች፡፡
በራፉን ከፍቶ ሲጨርስ መኪናዋን አንቀሰቀስችና ከግቢው እስወጣቻት..እሱም የከፈተውን በራፍ መልሶ ዘግቶ ሄዶ ተቀላቀላት፡፡
‹‹ ወደየት ልንዳው?››ጠየቀችው፡፡
‹‹ወደሜቅዶኒያ››
‹‹እርግጠኛ ነህ››ያልጠበቀችውን ስም ስለጠራላት ግራ ተጋባች..እሷ እንጦጦ ወይ አንድነት፤ካልሆም እስካይ ላይት እንደው ካነሰ ካነስ የሆነ ሲኒማ ወይም ቲያትር ቤት አንሂድ ይለኛል ብላ ነበር የጠበቀችው፡፡
..እንሂድ ወዳላት ቦታ ለመሄድ ብዙም ደስተኛ እንዳልሆነች በመገመት‹‹አዎ ምነው…?አባቴ እዛ ነው የሚኖረው ..በየሳምንቱ በዚህን ሰአት ይጠብቀኛል..ባይሆን ከዛ መልስ አንቺ የፈለግሽው ቦታ እንሄዳለን፡፡›አላት፡፡
‹‹አረ ችግር የለውም..እንዲሁ ያልጠበቅኩት ቦታ ስለሆነ ነው››ብላ በምትሄድበት ቦታ እንዳልተከፋች ተናገረች…እውነታው ግን እንደዛ አልነበረም፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ህያብ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
"ባልሽን አሳርፊው ልንማር እንጂ ልንሸረሙጥ አልመጣንም ቴሌግራም ላይ ሙሉ መረጃውን ታገኛለሽ" ይላል። እየተጠራጠርኩ ቴሌግራም ከፈትኩ ፊት ለፊት የመጣልኝን መልዕክት ስከፍተው
ፎቶ እና አጭር ቪድዮ..... ዮኒ ከሌላ ሴት ጋር....
እየሰሙ አለማመን ያለም የሚጠበቅም ነው። እያዩ አለማመን ግን ምን ይባላል። በአካል መጥተው ዮኒ ከእከሊት ጋር ማገጠብሽ ቢሉኝ አይደለም እሱን ልጠራጠር ከነገረኝ ሰው ጋር ልጣላ እችላለሁ። አሁን ግን እውነታ ነው ቁጭ ያለልኝ... ከምወደው ባሌ ጋር እርቃን ገላዋን አብራው የምታብድ ሴት እያየሁ ነው። የአንዷ አልበቃ ብሎ ከሌላ ሴት ጋር ደግሞ ከንፈሯ ላይ ተጣብቆ ያለ ፎቶ እያየሁ ነው... ግን አንድ ነገር ብቻ ነው የምለው። "የኔ ዮኒ አያደርገውም" አድርጎታል እኮ ...ግን ይህንን ማመን ያልፈለገ ውስጥ አለኝ... እናም እውነታውን እያየ ግግም ብሎ አላምን አለኝ። አንደኛው ውስጤ ደግሞ ፍቅርን ሳይቀር ወደጎን ብሎ በቀልን ፈለገ። ቢችል አሁን ያለበት ሄዶ ስጋውን ቢዘለዝለው ተመኘ። የማያምነው ውስጤ ገኖ ወጣና
"ዮኒ አያደርገውም" በጩኸት ቤቱን አደበላለኩት። ሰራተኛዬ እልፍነሽ መኝታ ቤቴን ከፈት አደረገችና
"ሰላም ነው ህያብ" አለችኝ
"ሰላም ነው እልፌ ወደ ስራሽ ተመለሽ" በሩን ዘግታ ተመለሰች። ረጅም ደቂቃ ዝምምም ብዬ ስልኬ ላይ አፈጠጥኩ
ሀሳቡ አደከመኝ ያየሁት እውነት አራደኝ በዛ ላይ ሰሞኑን የተለየ ኬዝ ስለነበረ ያለ እንቅልፍ ሆስፒታል ነበርኩ። ስልኬን ዘግቼ ያስቀመጥኩት መሰለኝ... ከዛ ወደ አልጋዬ ተራመድኩ.... አንድ.... ሁለት..... ጭልም አለብኝ።
"እናት ኧረ ንቂ የኔ ፍቅር" ይሄን ጥሪ ከሰማሁት ስንት አመት ሆነኝ.... ሁለት.... ሶስት... ብቻ በዛ መሀል... አሁንስ ለምንድነው እየሰማሁት ያለሁት... ሁሉም ነገር ከረፈደ... ካለፈበት በኋላ ለምን?... አይኔን ሳልገልጥ እንቅስቃሴውን እየተከታተልኩ ነው።
"ንገሪኝ እስኪ እናት ማነው ጥፋተኛ እኔ ወይስ አንቺ? በእርግጥ የኔ ጥፋት ሚዛን ይደፋል... ምክንያቱም ካየሽው ውጭ እንኳን ብዙ ጥፋቶችን ሰርቻለሁ ግን ባንቺ ጥፋት ላይ ተመርኩዤ ነው። ታውቂያለሽ ከቢኒ ጋር ድሮም እጠረጥርሽ ነበር እና ጥርጣሬዬን የሚያረጋግጥልኝ ነገር ሳገኝ እውነት አይደለም ብዬ ማመን አቃተኝ። ልታስረጅኝ ስትሞክሪ ውሸቷን ነው ብዬ አልሰማም አልኩሽ እናም ከዛን ጊዜ ጀምሮ ያለማቋረጥ ማገጥኩብሽ... ግን እናት ያሁኑ በደሌ በዛ..... (ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ እና ትንሽ ዝም ካለ በኋላ ቀጠለ) ከስንት ጊዜ በኋላ በአንዲት ልጅ ምክንያት ራሴን አዳመጥኩት። አብረሽኝ ካልተኛሽ ውጤትሽን አበላሸዋለሁ ብዬ አስፈራራኋት.... ብዙ ለመነችኝ... ልመናው አልሰራ ሲላት ግን ያንቺን አድራሻ ፈልጋ ሆስፒታል መጣችና አየችሽ። ስለትዳራችን ሳይቀር ብዙ መረጃ ሰበሰበች ከረፈደ ቢሆንም ንግግሯ ከእንቅልፌ አነቃችኝ... ትልቁን በደሌን የሰራሁ እለት ከእንቅልፌ ነቃሁ
'ሚስትህ ነፍሷን ሳትሰስት ትሰጥሀለች... አንተ ማመን ባልፈለከው ውሸት ውስጥ ተደብቀህ በሀጢያት ተጨማልቀሀል... ለሷ አትገባትም ምክንያቱም ንፁህ ናት... ግን እግዜር ይቅር የማይለው የለም አምላክህንም ሚስትህንም ይቅርታ ጠይቀህ ወደራስህ ተመለስ። ለውጤቴ ስል አብሬህ ላድር አልፈልግም በተለይ ያቺ ሚስኪ ላይ ይሄን ላደርግ አልችልም። ከፈለግህ ኤፍ አድርገው ህሊናዬን አላቆሽሽም' ብላኝ ስላንቺ እንዴት እንዳወቀች ሁሉንም ነገር አብራራችልን እና ለአመታት ከተኛሁበት እንቅልፍ ዛሬ ቀስቅሳኝ ሄደች። ያሰብኩት ለሀያ ደቂቃ ብቻ ነው። ወደራሴ ተመለስኩ... እውነታውን ማየት ቻልኩ... በንግግሮቼም ሆነ በተግባር ብዙ እንደገፋሁሽ አወቅሁ... በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን እንዴት እንደምትጠነቀቂልኝ... ምን ያክል እንደምትወጂኝ ተረዳሁ። ወደዚህ ለመምጣት እየተጣደፍኩ ስወጣ ቢሮ በር ላይ ከዚህ በፊት በውጤት አስፈራርቻት አብሪያት የተኛሁትን ልጅ አገኘኋት እናም ቪዲዮና ምስል ላንቺ እንደላከችልሽ ነገረችኝ። ምንም ሳልል ወደዚሁ መጣሁ ወድቀሽ አገኘሁሽ።
ህያቤቴ እየሰማሽኝ እንደሆነ አውቃለሁ። ይቅር በይኝ አልልሽም በተለይ በአንድ ጉዳይ ያንቺ ይቅርታ አይገባኝም... ብቻ አይንሽን ግለጪና የፈለግሺውን ቅጪኝ" አይኔን ገለጥኩ ከወገቤ ቀና አልኩና ትራስ ተደግፌ ቁጭ አልኩ። ለረጅም ደቂቃ በዝምታ አፈጠጥኩበት
"ደስ ያለሽን አድርጊኝ የፈለግሺውን ቅጪኝ " አንደበቴ ሊናገር ቢፈልግ እንኳን ውስጤ ዝምምምም ብሏል የሚያስፈራ ዝምታ
"ደግሞ አሁን እሰማሻለሁ ከቢኒ ጋር ያደረጋችሁትን ንገሪኝ እኔ እንደተናዘዝኩ ተናዘዢልኝ.... ይቅር ተባብለን አብረን ባንቀጥልም ጥያቄዎቼን እንድትመልሽልኝ እፈልጋለሁ... የምናሴ አባት ማነው። ህያብ አንቺም እኮ ድብቅ ነሽ ከኔ የደበቅሺው ብዙ ሚስጥር አለሽ" ዝምምምም
"እንቁን አሟት ነበር ልያት" ከመኝታ ቤታችን ወጥቼ ወደሷ ስሄድ
"እወቂ ለዚህ ሁሉ ነገር ያንቺም እጅ አለበት....ወይኔ አምላኬ ምንድነው ያደረኩት" ሰማሁት ግን ባልሰማ ወደ ልጄ ክፍል ሄድኩ
በሩን ከፈት አድርጌ ሳያት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝታለች ወደ ውስጥ ገባሁና ቀስ አድርጌ ዘጋሁት። የአልጋዋ ጫፍ ላይ ቁጭ ብዬ የትኛችውን እንቁዬን አየኋት ግንባሯ ላይ ቸፈፍ ያለ ላብ አለ። ፎጣ አንስቼ ስጠርግላት እጄን ለቀም አድርጋ ወረወረችውና
"እባክህ አትንካኝ እባክህ" ከእንቅልፏ ደንግጣ ነቃች
"ምንድነው ልጄ ማንን ነው አትንካኝ የምትይው"
"አይይ እእ....እ
"የምን እእ ነው ምንድነው ንገሪኝ" ለአመታት ስቃዥ የነበረው ትዝ አለኝ... አይ አይሆንም
"በህልሜ የሚያስፈራ ሰው ገደል ውስጥ ሊከተኝ ሲል አየሁ" ኡፍፍፍፍ.... እኔ ደግሞ ስንቱን አሰብኩት
"አሁን እንዴት ነው ቁርጠቱ ተሻለሽ" ዮኒ በሩን ከፍቶ ገባ
"ምን ሆነሽ ነው ምናሴ ብዙ አመመሽ እንዴ ጠዋት እኮ ረፍዶብኝ ሳላይሽ ሄድኩ" የቅድሙን የተፀፀተ ፊት ሳይሆን ፍም እሳት የሚተፋ አይኑን አየሁት... እንቁ ፊቷን አዙራ ተኛች
"ምንድነው አንቺ ባለጌ ለአባትሽ መልስ ስጪው እንጂ" ፊቷን እንዳዞረች
"ደና ነኝ ተሽሎኛል" አለችው። ተነሳሁና ትቻቸው ወጣሁ። ሳሎን ሶፋ ላይ ቁጭ ብዬ ቲቪው ላይ አፈጠጥኩ..... ሀሳቤ ግን ሩቅ ሄዶ ነበር። መች ነው ይሄን ክፍተት የፈጠርኩት... ለራሴ ደግሜ ልነግረው አልፈልግም የምለውን ያን የመደፈር ታሪኬን ከመደበቅ... አዎ ከዛ ነው የጀመርኩት... ከዛ የአዲስ አበባ ልጅ ነኝ አልኩት... ከዛ... ከዛ... ከቢኒ ጋር እንኳን ምንም ግንኙነት የለንም... እሱም እንዳስረዳው እድሉን አልሰጠኝም።
ቢዘገይም ነገሮችን አጥርቼ መሄድ እንዳለብኝ ተሰማኝ እና ታሪኬን ከአንድ ጀምሬ እነግረዋለሁ ብዬ ወሰንኩ... ግን አሁን አይደለም።
ህያብን ምን ይጨንቃታል ብትሉ ሰውን ተጣልቶ ማኩረፍ እላችኋለሁ። በህይወቴ እንደመኮራረፍ የምጠላው ነገር የለም አኩርፌ ማደርም አልችልም... በቃ ከሰው ጋ ተጋጨሁ አይደል ወይ እዛው ጋ ችግሩን እነግረዋለሁ ወይም ዝም ብዬ አልፈዋለሁ... ብቻ ያስከፋኝም ላስከፋውም ድጋሚ ሳገኘው ያንን ሰው አዋራዋለሁ። ከዮኒጋ በአንድ ጣራ ስር... አንድ አልጋ ላይ እየተኛን በየቀኑ እያየሁት ለማኩረፍ ሞከርኩ ግን አልተሳካልኝም በደሉን ባልረሳውም ሳላስበው አዋራሁት።
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በኤርሚ
"ባልሽን አሳርፊው ልንማር እንጂ ልንሸረሙጥ አልመጣንም ቴሌግራም ላይ ሙሉ መረጃውን ታገኛለሽ" ይላል። እየተጠራጠርኩ ቴሌግራም ከፈትኩ ፊት ለፊት የመጣልኝን መልዕክት ስከፍተው
ፎቶ እና አጭር ቪድዮ..... ዮኒ ከሌላ ሴት ጋር....
እየሰሙ አለማመን ያለም የሚጠበቅም ነው። እያዩ አለማመን ግን ምን ይባላል። በአካል መጥተው ዮኒ ከእከሊት ጋር ማገጠብሽ ቢሉኝ አይደለም እሱን ልጠራጠር ከነገረኝ ሰው ጋር ልጣላ እችላለሁ። አሁን ግን እውነታ ነው ቁጭ ያለልኝ... ከምወደው ባሌ ጋር እርቃን ገላዋን አብራው የምታብድ ሴት እያየሁ ነው። የአንዷ አልበቃ ብሎ ከሌላ ሴት ጋር ደግሞ ከንፈሯ ላይ ተጣብቆ ያለ ፎቶ እያየሁ ነው... ግን አንድ ነገር ብቻ ነው የምለው። "የኔ ዮኒ አያደርገውም" አድርጎታል እኮ ...ግን ይህንን ማመን ያልፈለገ ውስጥ አለኝ... እናም እውነታውን እያየ ግግም ብሎ አላምን አለኝ። አንደኛው ውስጤ ደግሞ ፍቅርን ሳይቀር ወደጎን ብሎ በቀልን ፈለገ። ቢችል አሁን ያለበት ሄዶ ስጋውን ቢዘለዝለው ተመኘ። የማያምነው ውስጤ ገኖ ወጣና
"ዮኒ አያደርገውም" በጩኸት ቤቱን አደበላለኩት። ሰራተኛዬ እልፍነሽ መኝታ ቤቴን ከፈት አደረገችና
"ሰላም ነው ህያብ" አለችኝ
"ሰላም ነው እልፌ ወደ ስራሽ ተመለሽ" በሩን ዘግታ ተመለሰች። ረጅም ደቂቃ ዝምምም ብዬ ስልኬ ላይ አፈጠጥኩ
ሀሳቡ አደከመኝ ያየሁት እውነት አራደኝ በዛ ላይ ሰሞኑን የተለየ ኬዝ ስለነበረ ያለ እንቅልፍ ሆስፒታል ነበርኩ። ስልኬን ዘግቼ ያስቀመጥኩት መሰለኝ... ከዛ ወደ አልጋዬ ተራመድኩ.... አንድ.... ሁለት..... ጭልም አለብኝ።
"እናት ኧረ ንቂ የኔ ፍቅር" ይሄን ጥሪ ከሰማሁት ስንት አመት ሆነኝ.... ሁለት.... ሶስት... ብቻ በዛ መሀል... አሁንስ ለምንድነው እየሰማሁት ያለሁት... ሁሉም ነገር ከረፈደ... ካለፈበት በኋላ ለምን?... አይኔን ሳልገልጥ እንቅስቃሴውን እየተከታተልኩ ነው።
"ንገሪኝ እስኪ እናት ማነው ጥፋተኛ እኔ ወይስ አንቺ? በእርግጥ የኔ ጥፋት ሚዛን ይደፋል... ምክንያቱም ካየሽው ውጭ እንኳን ብዙ ጥፋቶችን ሰርቻለሁ ግን ባንቺ ጥፋት ላይ ተመርኩዤ ነው። ታውቂያለሽ ከቢኒ ጋር ድሮም እጠረጥርሽ ነበር እና ጥርጣሬዬን የሚያረጋግጥልኝ ነገር ሳገኝ እውነት አይደለም ብዬ ማመን አቃተኝ። ልታስረጅኝ ስትሞክሪ ውሸቷን ነው ብዬ አልሰማም አልኩሽ እናም ከዛን ጊዜ ጀምሮ ያለማቋረጥ ማገጥኩብሽ... ግን እናት ያሁኑ በደሌ በዛ..... (ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ እና ትንሽ ዝም ካለ በኋላ ቀጠለ) ከስንት ጊዜ በኋላ በአንዲት ልጅ ምክንያት ራሴን አዳመጥኩት። አብረሽኝ ካልተኛሽ ውጤትሽን አበላሸዋለሁ ብዬ አስፈራራኋት.... ብዙ ለመነችኝ... ልመናው አልሰራ ሲላት ግን ያንቺን አድራሻ ፈልጋ ሆስፒታል መጣችና አየችሽ። ስለትዳራችን ሳይቀር ብዙ መረጃ ሰበሰበች ከረፈደ ቢሆንም ንግግሯ ከእንቅልፌ አነቃችኝ... ትልቁን በደሌን የሰራሁ እለት ከእንቅልፌ ነቃሁ
'ሚስትህ ነፍሷን ሳትሰስት ትሰጥሀለች... አንተ ማመን ባልፈለከው ውሸት ውስጥ ተደብቀህ በሀጢያት ተጨማልቀሀል... ለሷ አትገባትም ምክንያቱም ንፁህ ናት... ግን እግዜር ይቅር የማይለው የለም አምላክህንም ሚስትህንም ይቅርታ ጠይቀህ ወደራስህ ተመለስ። ለውጤቴ ስል አብሬህ ላድር አልፈልግም በተለይ ያቺ ሚስኪ ላይ ይሄን ላደርግ አልችልም። ከፈለግህ ኤፍ አድርገው ህሊናዬን አላቆሽሽም' ብላኝ ስላንቺ እንዴት እንዳወቀች ሁሉንም ነገር አብራራችልን እና ለአመታት ከተኛሁበት እንቅልፍ ዛሬ ቀስቅሳኝ ሄደች። ያሰብኩት ለሀያ ደቂቃ ብቻ ነው። ወደራሴ ተመለስኩ... እውነታውን ማየት ቻልኩ... በንግግሮቼም ሆነ በተግባር ብዙ እንደገፋሁሽ አወቅሁ... በእያንዳንዱ እንቅስቃሴያችን እንዴት እንደምትጠነቀቂልኝ... ምን ያክል እንደምትወጂኝ ተረዳሁ። ወደዚህ ለመምጣት እየተጣደፍኩ ስወጣ ቢሮ በር ላይ ከዚህ በፊት በውጤት አስፈራርቻት አብሪያት የተኛሁትን ልጅ አገኘኋት እናም ቪዲዮና ምስል ላንቺ እንደላከችልሽ ነገረችኝ። ምንም ሳልል ወደዚሁ መጣሁ ወድቀሽ አገኘሁሽ።
ህያቤቴ እየሰማሽኝ እንደሆነ አውቃለሁ። ይቅር በይኝ አልልሽም በተለይ በአንድ ጉዳይ ያንቺ ይቅርታ አይገባኝም... ብቻ አይንሽን ግለጪና የፈለግሺውን ቅጪኝ" አይኔን ገለጥኩ ከወገቤ ቀና አልኩና ትራስ ተደግፌ ቁጭ አልኩ። ለረጅም ደቂቃ በዝምታ አፈጠጥኩበት
"ደስ ያለሽን አድርጊኝ የፈለግሺውን ቅጪኝ " አንደበቴ ሊናገር ቢፈልግ እንኳን ውስጤ ዝምምምም ብሏል የሚያስፈራ ዝምታ
"ደግሞ አሁን እሰማሻለሁ ከቢኒ ጋር ያደረጋችሁትን ንገሪኝ እኔ እንደተናዘዝኩ ተናዘዢልኝ.... ይቅር ተባብለን አብረን ባንቀጥልም ጥያቄዎቼን እንድትመልሽልኝ እፈልጋለሁ... የምናሴ አባት ማነው። ህያብ አንቺም እኮ ድብቅ ነሽ ከኔ የደበቅሺው ብዙ ሚስጥር አለሽ" ዝምምምም
"እንቁን አሟት ነበር ልያት" ከመኝታ ቤታችን ወጥቼ ወደሷ ስሄድ
"እወቂ ለዚህ ሁሉ ነገር ያንቺም እጅ አለበት....ወይኔ አምላኬ ምንድነው ያደረኩት" ሰማሁት ግን ባልሰማ ወደ ልጄ ክፍል ሄድኩ
በሩን ከፈት አድርጌ ሳያት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝታለች ወደ ውስጥ ገባሁና ቀስ አድርጌ ዘጋሁት። የአልጋዋ ጫፍ ላይ ቁጭ ብዬ የትኛችውን እንቁዬን አየኋት ግንባሯ ላይ ቸፈፍ ያለ ላብ አለ። ፎጣ አንስቼ ስጠርግላት እጄን ለቀም አድርጋ ወረወረችውና
"እባክህ አትንካኝ እባክህ" ከእንቅልፏ ደንግጣ ነቃች
"ምንድነው ልጄ ማንን ነው አትንካኝ የምትይው"
"አይይ እእ....እ
"የምን እእ ነው ምንድነው ንገሪኝ" ለአመታት ስቃዥ የነበረው ትዝ አለኝ... አይ አይሆንም
"በህልሜ የሚያስፈራ ሰው ገደል ውስጥ ሊከተኝ ሲል አየሁ" ኡፍፍፍፍ.... እኔ ደግሞ ስንቱን አሰብኩት
"አሁን እንዴት ነው ቁርጠቱ ተሻለሽ" ዮኒ በሩን ከፍቶ ገባ
"ምን ሆነሽ ነው ምናሴ ብዙ አመመሽ እንዴ ጠዋት እኮ ረፍዶብኝ ሳላይሽ ሄድኩ" የቅድሙን የተፀፀተ ፊት ሳይሆን ፍም እሳት የሚተፋ አይኑን አየሁት... እንቁ ፊቷን አዙራ ተኛች
"ምንድነው አንቺ ባለጌ ለአባትሽ መልስ ስጪው እንጂ" ፊቷን እንዳዞረች
"ደና ነኝ ተሽሎኛል" አለችው። ተነሳሁና ትቻቸው ወጣሁ። ሳሎን ሶፋ ላይ ቁጭ ብዬ ቲቪው ላይ አፈጠጥኩ..... ሀሳቤ ግን ሩቅ ሄዶ ነበር። መች ነው ይሄን ክፍተት የፈጠርኩት... ለራሴ ደግሜ ልነግረው አልፈልግም የምለውን ያን የመደፈር ታሪኬን ከመደበቅ... አዎ ከዛ ነው የጀመርኩት... ከዛ የአዲስ አበባ ልጅ ነኝ አልኩት... ከዛ... ከዛ... ከቢኒ ጋር እንኳን ምንም ግንኙነት የለንም... እሱም እንዳስረዳው እድሉን አልሰጠኝም።
ቢዘገይም ነገሮችን አጥርቼ መሄድ እንዳለብኝ ተሰማኝ እና ታሪኬን ከአንድ ጀምሬ እነግረዋለሁ ብዬ ወሰንኩ... ግን አሁን አይደለም።
ህያብን ምን ይጨንቃታል ብትሉ ሰውን ተጣልቶ ማኩረፍ እላችኋለሁ። በህይወቴ እንደመኮራረፍ የምጠላው ነገር የለም አኩርፌ ማደርም አልችልም... በቃ ከሰው ጋ ተጋጨሁ አይደል ወይ እዛው ጋ ችግሩን እነግረዋለሁ ወይም ዝም ብዬ አልፈዋለሁ... ብቻ ያስከፋኝም ላስከፋውም ድጋሚ ሳገኘው ያንን ሰው አዋራዋለሁ። ከዮኒጋ በአንድ ጣራ ስር... አንድ አልጋ ላይ እየተኛን በየቀኑ እያየሁት ለማኩረፍ ሞከርኩ ግን አልተሳካልኝም በደሉን ባልረሳውም ሳላስበው አዋራሁት።
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
እናቷ ወ/ሪት በሬዱ በጣም ካፈቀረችው ..በጣም ከወደደችው…በጣም ካመለከችው ሰው ተኝታ ነው የፀነሰቻት…ግን ስለዚህ ሰውዬ ስታወራ …..ስለመልኩ ስትደሰኩር ..ስላሳለፉት የፍቅር ታሪክ ስትዘምር በልዩ መደነቅ እና በከፍተኛ ኩራት ቢሆንም ታሪኩን ከሚያዳምጧት ሰዎች መካከል 99.9 ፐርሰንቱ አያምኗትም…ሰው ሳይሆን ጋንኤልን ነበር ያፈቀረችው ይሏታል….ከዛም አለፍ ብለው ያፈቀረችው ብቻ ሳይሆን የፀነሰችውም ከዛው ጋንኤል ነው ብለው ይደመድማሉ፡፡ይሄ ሀሚት የሚጀመረው ደግሞ ከገዛ ዘመዶቾ ነው…ከዛ ጓረቤቶቾ ተቀበሉ እና ለከተማው ኑዋሪዎች በተኑት፡፡
ከጋንኤል ለመፀነሷ ማስረጃችን ብለው የሚያቀርቡት እንደሰው በዘጠኝ ወር መውለድ አለመቻሏ አንዱ ሲሆን ከዛም አልፎ ከእሷ የተወለደች ልጇ የጋንኤልን ጉልበትና ጥንካሬ ይዛ መወለዷን በመተንተን ማስረጃቸውን ያጠናክራሉ…ስለዚህ እንደእነሱ እምነት የእሷ ልዩ ብቃት ምንጩ ከጋንኤሉ አባቷ ዲ.ኤን.ኤ የወረስችው እንደሆነ እርግጠኛ ናቸው ....የቅርቧም ሆኑ የሩቆቹ ሰዎች ይሄንን አንስተው ሲያንሾካሹኩ ድንገት ስትደርስባቸው እና የሰማቻቸው ሲመስላቸው የምትበሳጭ እና የምትሸማቀቅ ይመስላቸውና ይደነግጣሉ..…እሷ ግን እንደውም ኩራት ነው የሚሰማት…አጠገቧ ሲሆኑ በጣም ትንሽነት ስለሚሰማቸውና ደካማነታቸውን ስለምታጎላባቸው ከሚሰማቸው የበታችነት ስሜት ለመላቀቅ የፈበረኩት ዘዴ አድርጋ ነው የምትወስደው፡፡
እውነትም ቢሆን ደግሞ ግድ የላትም… ‹‹ሰውና ጋንኤል ሲዳቀል እኔን የመሰለ በልዩ ችሎታና ኃይል የተሞላች ሰው ማለቴ ሰው እና ጋንኤል ማስገኘት ከቻለ…ጥሩ ነዋ ፡፡የስነ ህይወት ተመራማሪዎችስ በዳርዊን ቲዎሪ በመመራት የተሻለ ጥራት ያለው ዘር ለማግኘት አይደል ሁለት የተለያ ዘር አዳቅለው በማዋሀድ ሌላ የተሻለ ዘር ለማግኘት ሲጥሩ የሚታዩት (አንዳንዴ ውጤቱ በተቃራኒው ቢሆንም)››በማለት ማብራሪያ ትሰጣለች፡፡
ኬድሮን ልጅ ሆና ጀምሮ አንድ ሰው ሲያወራ እሷ ምታዳምጠው ሰውዬው በቃላት ከሽኖ የሚስተላልፈውን መልዕክት ሳይሆን በሚናገራቸው ቃላቶች አድበስብሶ ወደ ውስጡ ውጦ ያስቀራቸውን እና የደበቃቸውን ቃላቶች ተሰብስበው እና ተገጣጥመው አንድ ላይ በመጣመር የሚያስተላልፉትን መልዕክት ነው፡፡እሷ ምታዳምጠው ስሜቱን ነው…የፊቱን ቋጠር ፈታ ላይ የሚነበብበውን መልዕክት ፡፡....በዛ ደግሞ ከማንም ጋር በነፍሷ እንኳን ቢሆን አሲዛ መወዳደር ትችላለች…ሊነክሳት የመጣውንና ሊሰማት የመጣን ሰው ገና በኪሎ ሜትሮች ርቀት መለየት ትችላለች…በተለይ ማወቅ ፈልጋ ትኩረቷን ሰብስባ ትንሽ ካውጠነጠነች በቃ የሆነ መንፈስ አየሩን ሰንጥቆ በመምጣት ሚስጥሩን በጆሮዋ ሹክ ይላታል.በዚህ ተአምራዊ ክስተት አይደለም ሌላ ሰው እሷ እራሷ በራሷ ትደመማለች፡፡…
ኬድሮን ከውልደቷ ሚስጥር ማነፍነፍ ፤የሰውን ገበና መበርበር፤ የወዳጆችን ሹክሹክታ መጥለፍ ዋና ባህሪዋ ነው፡፡ከምግብ እኩላ ሚስጥር ነው የሚያኖራት፡፡ከመጋረጃ ጀርባ የሚካሄድ ድርጊቶችን ማነፍነፍ የተፈጠረችበት ዋና የህይወቷ አላማ ይመስላል፡፡
ኬድሮን አምስት አመቷ ላይ ነው የ10 አመት አጎቷን ተከትላ ትምህርት ቤት የሄደችው፡፡በወቅቱ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ዘመድ ስለነበር ተዋት አንድ ሳምንት አብራው ዝም ብላ ትቀመጥና ከዛ እራሷ ሰልችቷት ይቅርብኝ ትላለች ብሎ ፈቀደላት… አንድ ወር ተመላለሰቸ…ሁለት ወር ተመላለሰች… ተማሪዎችም ሆኑ አስተማሪዎች ረሷትና ልክ እንደመደበኛ ተማሪ ያዮት ጀመር…ቀስ እያለ ተአምራዊነቷ ቀጠለ..ፈተና አብራ ስትፈተን የምትስተው ጥያቄ አልነበረም…አንደኛ ሴሚስተር ፈተና ወስዳ ካርድ ሲሰጠጥ በሮስተሩ ላይ የአንደኝነቱን ቦታ የያዘችው እሷ ነበረች…መነጋገሪያ ሆነች…ሁለተኛ ሴሚስተር ሲጀመር ሶስተኛ ክፍል ሄዳ ተቀመጠች ፤አረ ወደ ክፍልሽ ተመለሽ ብትባልም ማንንም አልሰማችም…ውጤቷ እንደሌላው ተማሪ በሮስተር ላይ ባይሰፍርም ለብቻ ግን ተሰራ .. በአመቱ መጨረሻም ከሶስተኛ ክፍል በሁለተኛ ሴሚስተር ትልቁን ውጤት ያመጣችው እሷ ሆና ተገኘች፡፡
በእሷ ጉዳይ የትምህርት ቤቱ አስተዳደርና መምህራኖቹ ስብሰባ ተቀመጡ ‹‹እንዴት እናድርጋት…?››
በቃ ችሎታዋ የተመሰከረለት ነው…እድሜዋ ግን ገና ስድስት አመቷ ነው..ቢሆንም ኃላፊነቱን እንውሰድና በሚቀጥለው ሶስተኛ ክፍል አንድ ብላ ትጀምር ተብሎ ተወሰነ፡፡ ይሄንን በደስታ ነገሯት…፡፡ሶስተኛ ክፍል እንድትገባ የተወሰነበትን ካርድ ሰጧት . እሷ ግን አልተስማማችም….እሱን ይዛ እቤቷ ቀረች፤.በጣም የሚወዷት አስተማሪዎች እቤት ድረስ መጥተው እናቷና ወላጆቾ ፊት እንደትልቅ ሰው ኮሰተር ብለው እየተቆጧት ደግሞም እንደህፃን ለሰስለስብ እያባበሏት አናገሯት..‹‹ዘንድሮ መማር አልፈልግም ከብት ብጠብቅ ይሻለኛል…፡፡ስድስተኛ ክፍል ካስገባችሁኝ ግን እማራለሁ ››አለች…እነሱም ‹‹አይ.እንኳን ስደስተኛ ክፍል ሶስተኛውም እንደሚያስጠይቀን እያወቅን ነው››አሉ ፡፡ እሷም በአቋሟ ፀናችና በሰባተኛ አመቷ የሶስተኛ ክፍል ካርድ ይዛ እረኝነት ጀመረች፡፡
ጥዋት ትነሳና እናቷ የሰራችላትን ቁርስ በልታ፤ ምሳዋና በሰሀን ቋጥራ ከብቶችን ከበረት ታወጣና ላሞችንም አህዬችንም በግና ፍሎችን ጨምሮ ከ20 በላይ የሆኑ የቤተሰቦቾን ከብቶች ይዛ ወደ ጫካ ጉዞ ትጀምራለች፤ ለመጀመሪያ ሁለት ወር ያህል ከቤቱ አንድ ትልቅ ሰው ይከተላትና አብሯት ይውል ነበር….በኃላ ግን ነገረ ስራዋንና ሲያዩ ‹‹እሷ ብቻዋን ሳትሆን መንፈስም በላዮ ላይ ስላለ ለምን እንለፋለን ››ብለው ሙሉ በሙሉ ተውላት፡፡በዛ ላይ እሷ ባለችበት ቦታ የከተማው እረኛ ሁሉ ስለሚሰበሰብና እርስ በርስ ስለሚረዳዱ አስተማማኝ እረኛ ሆነች…
በአካባቢው በእሷ እድሜ ያሉ ግቢ ውስጥ የተሰጣ እህል ዶሮች ወይም ከብቶች እንዳይበሉ እንዲጠብቁ ይደረጋሉ...ጎረቤት ሄደው ቡና እንዲጠሩ ወይም እቃ እንዲያመጡ ይታዘዛሉ…ቄስ ትምህርት ቤት ሄደው ፊደል እንዲቆጥሩ ይላካሉ…ኬድሮን የምትሰራውን ስራ የሚሰሩ ልጆች ግን በብዛት እድሜያቸው ከ12-16 ያሉ ታዳጊዎች ናቸው፡፡እሷ ግን የራሳቸው ከብቶች ብቻ ሳይሆኑ የጎሮቤት ከብቶች ሳይቀሩ ድምጾን ይለዮታል.. በሚያስገርም ሁኔታም ድምፃን ሰምተውና ትዕዛዞን ተቀብለው ይታዘዞታል፡፡
ኬድሮን እረኝነቷ ብቻ አይደለም ሚገርመው..አደገኛ አዳኝ፤ምርጥ አትክልተኛ እና አሳ አስጋሪ ነች፡ማታ ወደቤቷ ስትመለስ በአንዱ አህያ ጀርባ ላይ ለማገዶ የሚሆን እንጨት ጭና፤ በተከሻዋ ወይም ጅግራ..ወይ ቆቅ ካልሆነም ዓሣ...አንዳንዴም ከየዛፍ ሚቀነጠሱና የሚሸመጠጡ የጫካ ፍራፍሬዎች እሮቃ፤ ቀጋ፤ አጋም፤ ኮምጣጤ፤ጊሽጣ፤ብቻ የሆነ አንድ የሚበላ ነገር በቀሚሷጫፍ ቋጥራ ፤መምጣት የዘወትር ተግባሯ ነው፡፡
በቀን ለአንድና ለሁለት ሰዓት ደግሞ ከብቶቾን ለጓደኞቾ አደራ ሰጥታ ወላጆቾ በያዶት ወንዝ ዳር ወዳላቸው የመስኖ እርሻ ጎራ ትልና..ሸንኮራውን ኮትኩታ፤ሙዙን ተንከባክባ …መንደሪኑን ውሀ አጠጥታ..ከቻለችውና ካሰኛት ቀንጠስ ቀንጠስ አድርጋ የተወሰነውን በልታ የተወሰነውን ለጓደኞቾ ይዛ ወደከብቶቾ መመለስ ከተለመዱ ስራዎቾ መካከል አንድ ነው፡፡በዚህ የተነሳ ቤቱ ውስጥ እንደ 40 አመት ጎልማሳና የቤቱ ዋና ስተዳዳሪ ተደርጋ ነው ምትታሰበው…ምትናገረውን እንደትልቅ ሰው ያደምጧታል ፤ምትሰጠውን ምክር አሮጊቶቹ ሳይቀሩ ተቀብለው ተግባራዊ ያደርጋሉ፤ችግር ሲገጥማቸውም ቀድመው የሚያማክሯት ለእሷ ነው፡፡የሁሉንም ችግር በፅሞና ከሰማች በኋላ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
እናቷ ወ/ሪት በሬዱ በጣም ካፈቀረችው ..በጣም ከወደደችው…በጣም ካመለከችው ሰው ተኝታ ነው የፀነሰቻት…ግን ስለዚህ ሰውዬ ስታወራ …..ስለመልኩ ስትደሰኩር ..ስላሳለፉት የፍቅር ታሪክ ስትዘምር በልዩ መደነቅ እና በከፍተኛ ኩራት ቢሆንም ታሪኩን ከሚያዳምጧት ሰዎች መካከል 99.9 ፐርሰንቱ አያምኗትም…ሰው ሳይሆን ጋንኤልን ነበር ያፈቀረችው ይሏታል….ከዛም አለፍ ብለው ያፈቀረችው ብቻ ሳይሆን የፀነሰችውም ከዛው ጋንኤል ነው ብለው ይደመድማሉ፡፡ይሄ ሀሚት የሚጀመረው ደግሞ ከገዛ ዘመዶቾ ነው…ከዛ ጓረቤቶቾ ተቀበሉ እና ለከተማው ኑዋሪዎች በተኑት፡፡
ከጋንኤል ለመፀነሷ ማስረጃችን ብለው የሚያቀርቡት እንደሰው በዘጠኝ ወር መውለድ አለመቻሏ አንዱ ሲሆን ከዛም አልፎ ከእሷ የተወለደች ልጇ የጋንኤልን ጉልበትና ጥንካሬ ይዛ መወለዷን በመተንተን ማስረጃቸውን ያጠናክራሉ…ስለዚህ እንደእነሱ እምነት የእሷ ልዩ ብቃት ምንጩ ከጋንኤሉ አባቷ ዲ.ኤን.ኤ የወረስችው እንደሆነ እርግጠኛ ናቸው ....የቅርቧም ሆኑ የሩቆቹ ሰዎች ይሄንን አንስተው ሲያንሾካሹኩ ድንገት ስትደርስባቸው እና የሰማቻቸው ሲመስላቸው የምትበሳጭ እና የምትሸማቀቅ ይመስላቸውና ይደነግጣሉ..…እሷ ግን እንደውም ኩራት ነው የሚሰማት…አጠገቧ ሲሆኑ በጣም ትንሽነት ስለሚሰማቸውና ደካማነታቸውን ስለምታጎላባቸው ከሚሰማቸው የበታችነት ስሜት ለመላቀቅ የፈበረኩት ዘዴ አድርጋ ነው የምትወስደው፡፡
እውነትም ቢሆን ደግሞ ግድ የላትም… ‹‹ሰውና ጋንኤል ሲዳቀል እኔን የመሰለ በልዩ ችሎታና ኃይል የተሞላች ሰው ማለቴ ሰው እና ጋንኤል ማስገኘት ከቻለ…ጥሩ ነዋ ፡፡የስነ ህይወት ተመራማሪዎችስ በዳርዊን ቲዎሪ በመመራት የተሻለ ጥራት ያለው ዘር ለማግኘት አይደል ሁለት የተለያ ዘር አዳቅለው በማዋሀድ ሌላ የተሻለ ዘር ለማግኘት ሲጥሩ የሚታዩት (አንዳንዴ ውጤቱ በተቃራኒው ቢሆንም)››በማለት ማብራሪያ ትሰጣለች፡፡
ኬድሮን ልጅ ሆና ጀምሮ አንድ ሰው ሲያወራ እሷ ምታዳምጠው ሰውዬው በቃላት ከሽኖ የሚስተላልፈውን መልዕክት ሳይሆን በሚናገራቸው ቃላቶች አድበስብሶ ወደ ውስጡ ውጦ ያስቀራቸውን እና የደበቃቸውን ቃላቶች ተሰብስበው እና ተገጣጥመው አንድ ላይ በመጣመር የሚያስተላልፉትን መልዕክት ነው፡፡እሷ ምታዳምጠው ስሜቱን ነው…የፊቱን ቋጠር ፈታ ላይ የሚነበብበውን መልዕክት ፡፡....በዛ ደግሞ ከማንም ጋር በነፍሷ እንኳን ቢሆን አሲዛ መወዳደር ትችላለች…ሊነክሳት የመጣውንና ሊሰማት የመጣን ሰው ገና በኪሎ ሜትሮች ርቀት መለየት ትችላለች…በተለይ ማወቅ ፈልጋ ትኩረቷን ሰብስባ ትንሽ ካውጠነጠነች በቃ የሆነ መንፈስ አየሩን ሰንጥቆ በመምጣት ሚስጥሩን በጆሮዋ ሹክ ይላታል.በዚህ ተአምራዊ ክስተት አይደለም ሌላ ሰው እሷ እራሷ በራሷ ትደመማለች፡፡…
ኬድሮን ከውልደቷ ሚስጥር ማነፍነፍ ፤የሰውን ገበና መበርበር፤ የወዳጆችን ሹክሹክታ መጥለፍ ዋና ባህሪዋ ነው፡፡ከምግብ እኩላ ሚስጥር ነው የሚያኖራት፡፡ከመጋረጃ ጀርባ የሚካሄድ ድርጊቶችን ማነፍነፍ የተፈጠረችበት ዋና የህይወቷ አላማ ይመስላል፡፡
ኬድሮን አምስት አመቷ ላይ ነው የ10 አመት አጎቷን ተከትላ ትምህርት ቤት የሄደችው፡፡በወቅቱ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ዘመድ ስለነበር ተዋት አንድ ሳምንት አብራው ዝም ብላ ትቀመጥና ከዛ እራሷ ሰልችቷት ይቅርብኝ ትላለች ብሎ ፈቀደላት… አንድ ወር ተመላለሰቸ…ሁለት ወር ተመላለሰች… ተማሪዎችም ሆኑ አስተማሪዎች ረሷትና ልክ እንደመደበኛ ተማሪ ያዮት ጀመር…ቀስ እያለ ተአምራዊነቷ ቀጠለ..ፈተና አብራ ስትፈተን የምትስተው ጥያቄ አልነበረም…አንደኛ ሴሚስተር ፈተና ወስዳ ካርድ ሲሰጠጥ በሮስተሩ ላይ የአንደኝነቱን ቦታ የያዘችው እሷ ነበረች…መነጋገሪያ ሆነች…ሁለተኛ ሴሚስተር ሲጀመር ሶስተኛ ክፍል ሄዳ ተቀመጠች ፤አረ ወደ ክፍልሽ ተመለሽ ብትባልም ማንንም አልሰማችም…ውጤቷ እንደሌላው ተማሪ በሮስተር ላይ ባይሰፍርም ለብቻ ግን ተሰራ .. በአመቱ መጨረሻም ከሶስተኛ ክፍል በሁለተኛ ሴሚስተር ትልቁን ውጤት ያመጣችው እሷ ሆና ተገኘች፡፡
በእሷ ጉዳይ የትምህርት ቤቱ አስተዳደርና መምህራኖቹ ስብሰባ ተቀመጡ ‹‹እንዴት እናድርጋት…?››
በቃ ችሎታዋ የተመሰከረለት ነው…እድሜዋ ግን ገና ስድስት አመቷ ነው..ቢሆንም ኃላፊነቱን እንውሰድና በሚቀጥለው ሶስተኛ ክፍል አንድ ብላ ትጀምር ተብሎ ተወሰነ፡፡ ይሄንን በደስታ ነገሯት…፡፡ሶስተኛ ክፍል እንድትገባ የተወሰነበትን ካርድ ሰጧት . እሷ ግን አልተስማማችም….እሱን ይዛ እቤቷ ቀረች፤.በጣም የሚወዷት አስተማሪዎች እቤት ድረስ መጥተው እናቷና ወላጆቾ ፊት እንደትልቅ ሰው ኮሰተር ብለው እየተቆጧት ደግሞም እንደህፃን ለሰስለስብ እያባበሏት አናገሯት..‹‹ዘንድሮ መማር አልፈልግም ከብት ብጠብቅ ይሻለኛል…፡፡ስድስተኛ ክፍል ካስገባችሁኝ ግን እማራለሁ ››አለች…እነሱም ‹‹አይ.እንኳን ስደስተኛ ክፍል ሶስተኛውም እንደሚያስጠይቀን እያወቅን ነው››አሉ ፡፡ እሷም በአቋሟ ፀናችና በሰባተኛ አመቷ የሶስተኛ ክፍል ካርድ ይዛ እረኝነት ጀመረች፡፡
ጥዋት ትነሳና እናቷ የሰራችላትን ቁርስ በልታ፤ ምሳዋና በሰሀን ቋጥራ ከብቶችን ከበረት ታወጣና ላሞችንም አህዬችንም በግና ፍሎችን ጨምሮ ከ20 በላይ የሆኑ የቤተሰቦቾን ከብቶች ይዛ ወደ ጫካ ጉዞ ትጀምራለች፤ ለመጀመሪያ ሁለት ወር ያህል ከቤቱ አንድ ትልቅ ሰው ይከተላትና አብሯት ይውል ነበር….በኃላ ግን ነገረ ስራዋንና ሲያዩ ‹‹እሷ ብቻዋን ሳትሆን መንፈስም በላዮ ላይ ስላለ ለምን እንለፋለን ››ብለው ሙሉ በሙሉ ተውላት፡፡በዛ ላይ እሷ ባለችበት ቦታ የከተማው እረኛ ሁሉ ስለሚሰበሰብና እርስ በርስ ስለሚረዳዱ አስተማማኝ እረኛ ሆነች…
በአካባቢው በእሷ እድሜ ያሉ ግቢ ውስጥ የተሰጣ እህል ዶሮች ወይም ከብቶች እንዳይበሉ እንዲጠብቁ ይደረጋሉ...ጎረቤት ሄደው ቡና እንዲጠሩ ወይም እቃ እንዲያመጡ ይታዘዛሉ…ቄስ ትምህርት ቤት ሄደው ፊደል እንዲቆጥሩ ይላካሉ…ኬድሮን የምትሰራውን ስራ የሚሰሩ ልጆች ግን በብዛት እድሜያቸው ከ12-16 ያሉ ታዳጊዎች ናቸው፡፡እሷ ግን የራሳቸው ከብቶች ብቻ ሳይሆኑ የጎሮቤት ከብቶች ሳይቀሩ ድምጾን ይለዮታል.. በሚያስገርም ሁኔታም ድምፃን ሰምተውና ትዕዛዞን ተቀብለው ይታዘዞታል፡፡
ኬድሮን እረኝነቷ ብቻ አይደለም ሚገርመው..አደገኛ አዳኝ፤ምርጥ አትክልተኛ እና አሳ አስጋሪ ነች፡ማታ ወደቤቷ ስትመለስ በአንዱ አህያ ጀርባ ላይ ለማገዶ የሚሆን እንጨት ጭና፤ በተከሻዋ ወይም ጅግራ..ወይ ቆቅ ካልሆነም ዓሣ...አንዳንዴም ከየዛፍ ሚቀነጠሱና የሚሸመጠጡ የጫካ ፍራፍሬዎች እሮቃ፤ ቀጋ፤ አጋም፤ ኮምጣጤ፤ጊሽጣ፤ብቻ የሆነ አንድ የሚበላ ነገር በቀሚሷጫፍ ቋጥራ ፤መምጣት የዘወትር ተግባሯ ነው፡፡
በቀን ለአንድና ለሁለት ሰዓት ደግሞ ከብቶቾን ለጓደኞቾ አደራ ሰጥታ ወላጆቾ በያዶት ወንዝ ዳር ወዳላቸው የመስኖ እርሻ ጎራ ትልና..ሸንኮራውን ኮትኩታ፤ሙዙን ተንከባክባ …መንደሪኑን ውሀ አጠጥታ..ከቻለችውና ካሰኛት ቀንጠስ ቀንጠስ አድርጋ የተወሰነውን በልታ የተወሰነውን ለጓደኞቾ ይዛ ወደከብቶቾ መመለስ ከተለመዱ ስራዎቾ መካከል አንድ ነው፡፡በዚህ የተነሳ ቤቱ ውስጥ እንደ 40 አመት ጎልማሳና የቤቱ ዋና ስተዳዳሪ ተደርጋ ነው ምትታሰበው…ምትናገረውን እንደትልቅ ሰው ያደምጧታል ፤ምትሰጠውን ምክር አሮጊቶቹ ሳይቀሩ ተቀብለው ተግባራዊ ያደርጋሉ፤ችግር ሲገጥማቸውም ቀድመው የሚያማክሯት ለእሷ ነው፡፡የሁሉንም ችግር በፅሞና ከሰማች በኋላ
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
...ከጊዜ ማህፀን ውስጥ አስደናቂና አሰቃቂ የህይወት ታአምራቶች ተፀንሰው ሲወለዱ ታዝበናል፡፡
የግቢውን በር ዘበኛው እንደከፈተለት መኪናውን ቦታ አስይዞ ለመቆም እንኳን ትዕግስት አልነበረውም፡፡ ሞተሩን አጠፋና እየተንደረደረ ወደ ቤት ገባ፡፡ የውብዳር ብቻዋን መለስተኛ አዳራሽ በሚያክለው ሳሎን ቁጭ ብላ በባለ 36 ኢንች ፍላትስክሪን ሶኒ ቴሌቭዥን ፊልም እየተመለከተች ነው፡፡ ሊያናግራትም አልፈለገም፡፡ዞር ብሎም አላያትም፡፡ ሳሎኑን ሰንጥቆ መኝታ ቤቱ የገባው ላፕቶፑን ፍለጋ ነበር፡፡ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ ከፈተው፡፡ ዲስኩን አውጥቶ ከተተውና እስኪጫወትለት መጠበቅ ጀመረ፡፡ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፡፡
አምስት ሺ ብር ያወጣበት መረጃ ነው፡፡ ላለፉት ሦስት ቀናቶች ሠው ቀጥሮ ሚስቱን ሲያሰልላት ነበር፡፡ ቅጥረኞቹ ባዘዛቸው መሰረት ተከታትለዋታል፡፡ አዋዋሏን ቀርፀው ሙሉ መረጃውን በማስረከብ ብራቸውን ተቀብለው ተሰናብተውታል፡፡ በአንደበታቸው የነገሩት ነገር ባለመኖሩ ምስሉን አይቶ ጥርጣሬውን ከአዕምሮው እስኪፍቅ ቸኩሏል፡፡ሠሎሞን የውብዳርን ለማሠለል የወሰነበት ምክንያት ፀባይዋ፣ አለባበሷ፣አነጋገሯ ጠቅላላ ሁኔታዋ ከበፊቱ በተጋነነ ሁኔታ እየተለወጠ ስለመጣበት ነው፡፡ በእርግጥ መጣላትና መናቆር ከጀመሩ ዓመታት ቢቆጠርም እንደ አለፉት ሦስት ወራቶች ነገሮች መጠን አልፈው አያውቁም፡፡ በዚህም የተነሳ ስድስተኛ የስሜት ህዋሱ እንዲከታተላት ሹክ አለው፡፡
ኮምፒውተሩ መጫወት ጀመረ፡፡ መናፈሻ ቦታ ነው፡፡ ያምራል፡፡ ግቢው በዛፎች እና በአበቦች የደመቀ ነው፡፡ ትክክለኛ ቦታውን መለየት አልቻለም፡፡ የውብዳር የሚያምር ነጭ የፕላስቲክ ወንበር ላይ ተቀምጣለች፡፡ ከጎኗ የወንድ እግር ይታያል፡፡ ፊት ለፊታቸው ለስላሳ መጠጦችና በርገር ተቀምጧል፡፡ፊልሙ ተንቀሳቀሰ፡፡ የወንድየው እጅ ወደ የውብዳር ሰውነት ተንቀሳቀሰ ፡፡ እጁን እጇ ላይ አርጎ ያሻሻታል፡፡ ቀስ በቀስ የሠውዬው አካል እየታየ መጣ፡፡ እስከ ወገብ .. እስከ ደረቱ .. ፊቱ ከመጋለጡ በፊት ግን ነጭ የደንብ ልብስ የለበሰች አስተናጋጅ እፊት ለፊት ተደንቅራ ስክሪኑን ሞላችው፡፡‹‹ብሽቅ›› አለ ሠሎሞን፣የማወቅ ጥሙን በፍጥነት ማርካት ስላልቻለ ተበሳጭቶ፡፡
ከውስን ደቂቃዎች መቋረጥ በኋላ ፊልሙ ዳግም መጫወት ጀመረ፡፡ ሆቴል ውስጥ ነው፡፡ የሁለተኛ ቀን ቀረፃ መሆኑ የሚያስታውቀው የለበሠችው ልብስ የተለየ በመሆኑ ነው፡፡ አለባበሷ ወደ ግማሽ እርቃንነት ያዘነበለ ነው፡፡ አብሯት ያለው ወንድ ማንነት ወዲውኑ ነበር በእስክሪኑ ፊት ብቅ እንዳለ የለየው፡፡ በደንብ ያውቀዋል፡፡ ሹፌሯ ነው፡፡ ተንፈስ አለ፡፡ ማየቱን ግን አላቆመም፡፡ ቀጠለ፡፡ ሁለቱም ፊት ለፊት በማራኪ ብርጭቆ ውስኪ ቀርቧል፡፡ ግራ ገባው፡፡ ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡ በሳቅ የታጀበ ወሬ ያወራሉ፡፡
ምስሉ ድምፅ አልባ ቢሆንም የከንፈር እንቃስቃሴያቸው ሲታይ፣ በአብዛኛው እሱ ያወራላታል እሷ ትንከታከታለች፡፡ነገሮች
በተመሳሳይ ሁኔታ ለደቂቃዎች ከቀጠሉ በኋላ
አይን የሚስብ ነገር ድንገት ተመለከተ፡፡
የሹፌሩ እጅ በጠረጴዛው ስር አሻግሮ ወደ የውብዳር ጭን እያመራ ነው….፡፡ የለበሰችውን አጭር ጉርድ ቀሚስ ወደ ላይ ገፋ አድርጎ ማሻሸት ጀመረ፡፡ እሷም ግራና ቀኟን ተገላምጣ ከተመለከተች በኋላ ብሩህ የሆነ ፈገግታ ለግሳው፣ ከመቀመጫዋ ወደ ፊት ሸርተት ብላ ተጠጋችለት፡፡ ጣቶቹን ጭኖቿ መሀል ሰነቀራቻውና ማርመስመስ ጀመረ፡፡ ተጋጥመው የነበሩትን እግሮቿን ቀስ በቀስ እያላቀቀች... እየከፈተች መጣች፡፡ መረጋጋት እንዳልቻለች ከፊቷ መቀያየር መረዳት ይቻላል፡፡
ከንፈሮቿ ለንግግር በዝግታ ተነቃነቁ፡፡ የሆነ ነገር መለሰላትና እጆቹን ሰብስቦ አስተናጋጁን ጠራ፡፡ የማይሰማ ነገር እየነገረው እጁን ወደ ኪሱ ሠደደ፡፡እሷ ቀድማ ቦርሳዋ ገባችና
የተወሰኑ የብረ ኖቶችን አውጥታ ቀድማ ለአስተናጋጁ ሠጠችው፡፡
አስተናጋጁ እየተንደረደረ እንግዳ መቀበያ ቢሮ ሲገባ ታየ፡፡ ዳግመኛ እጁን ወደ ጭኖቿ አላከም፡፡ይልቁንም ወደ መጠጡ ሠደደና
ደጋግሞ ይጎነጭ ጀመር፡፡
እሷም ተመሳሳዩን እርምጃ ወሰደች የተወሰነ ደቂቃ ካጠፋ በኋላ አስተናጋጁ ተመልሶ መጣና የማይሰማ ነገር ነገራቸው፡፡ ዝርዝር ብሮች አውጥቶ አስጨበጠውና እጆቿን ይዞ ከተቀመጠችበት አስነሳት፡፡ ወገቧን አቀፈና በጓሮ በር
ይዟት ወጣ። ፊልሙ ተቋረጠ፡፡ ሠሎሞን ላፕቶፑን
ወርውሮ
ከግድግዳ ጋር ሊያላትመው ፈለገ፡፡
ስሜቱን መቆጣጠር እየተሳነው መጥቷል፡፡ በዛ ሠፊ ሆዱ ሙሉ እሳት እየነደደበት ነው፡፡ፊልሙ መጫወቱን ቀጥሎል፡፡ አሁንም ወገቧን እንዳቀፋት ነው፡፡ የሆነ ፎቅ ደረጃ እየወጡ ነው፡፡ በመደዳ የተደረደሩ በሮች ይታያሉ፡፡
የተወሰኑትን ክፍሎች አልፈው ከሄዱ በኋላ ቆሙ፡፡ 2ዐ3 ቁጥር የተለጠፈበት ክፍል አጠገብ ሲደርሱ ከፍቶ ወደ ውስጥ ጎተታት፡፡ እየተፍለቀለቀች ተጎተተችለት፡፡ ቦርሳዋን ወለል ላይ ጥላ ጫማዋን ለማውለቅ ስትጣደፍ ይታያል፡፡ ትእይንቱ ከዚህ በላይ መቀጠል አልቻለም፡፡ በራፉ ከውስጥ ተዘጋ፡፡ጠቅላላ ሠውነቱ ላይ ውሃ እንደከለበሱበት ሠው በላብ ተጠመቀ፡፡ ምን ማድረግ እንዳለበት ማሠብ እንኳን ተሳነው፡፡ መጮኽ... ማበድ... ዕቃ መስበር አሠኘው፡፡ ከሁሉ ነገር በላይ ፊት ለፊት መታለሉ አበገነው፡፡
፨፨፨
የውብዳር ሹፌር ያስፈልገኛል ብላ የጠየቀችው ከአምስት ወር በፊት ነበር፡፡እሷ እራሷ መንዳት እየቻለች ሹፌር ለምን እንዳስፈለጋት ሲጠይቃት፤ ከልብ ድካም በሽታዋ ጋር በተያያዘ ሀኪም ላልተወሠነ ጊዜ መንዳት እንደከለከላት ነበር ያስረዳችው፡፡ ለጉዳዩ ብዙም ትኩረት ሳይሰጠው ፡
‹‹ታዲያ ፈልጊና ቅጠሪያ ምን ችግር አለው፤ ገንዘብ እንደሆነ አለሽ›› ነበር ያላት፡፡
‹‹ገንዘብ ማን ጠየቀህ? የምታውቀው ደህና ሹፌር ካለ እንድታናግርልኝ እንጂ..፡፡››
‹‹እኔ በአንዲት ቀበጥ ወይዘሮ ትእዛዝ በየሱፐር ማርኬትና በየፀጉር መፈሸኛ ቤት ሲንከራተት ለመዋል ትዕግስት ያለው ሹፌር አላውቅም፡፡››
‹‹ባንተ ቤት አሽሙር ተናግረህ ልብህ ውልቅ ብሎል፡፡ በአጭሩ አልችልም ወይም ፍላጎት የለኝም አትልም፡፡ ይብላኝ ላንተ እንጂ ችግር የለውም፡፡ ካገኘሁ አገኘሁ ካላገኘው ደግሞ ለጊዜውም ቢሆን በታክሲ እጠቀማለሁ፡፡ ልጆቹን ወደ ት/ቤት የማመላለሱን ጉዳይ ግን አስብበት›› በማለት ነበር እየተቆናጠረች በቆመበት ጥላው የሄደችው፡፡
ሹፌሩ ተገኝቶ መኪናውን ለመያዝ ግን ሁለት ቀን ብቻ ነበር የፈጀበት፡፡ ከየት አገኘሽው? በስንት ብር ቀጠርሽው? የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አልጠየቃትም፡፡ ሹፌሩ የሃያ አራት ዓመት ገደማ አፍላ ጎረምሳ ነው፡፡ ‹‹ሳምሶን እባላለሁ›› ነበር ያለው በመጀመሪያ ቀን ሲተዋወቀው፡፡ ሚስቱና ልጆቹ ግን ሳሚ እያሉ ነው በቁልምጫ የሚጠሩት፡፡ ስራ እንደጀመረ ሰሞን ነገረ ስራው ሁሉ ባይጥመውም፣ ዋል አደር ሲል ግን ለልጆቹ የሚያደርገውን እንክብካቤና ልጆቹም ምን ያህል በፍቅር እንደተቀበሉት ሲገነዘብ ቅሬታውን ችላ ብሎ ተወው፡፡ይሄዋ ዛሬ ችላ የማለቱን ፍሬ እየተመለከተ ነው፡፡
ላፕቶፑን እንደያዘ እየተንደረደረ ወደ ሳሎን ሄደ፡፡ የውብዳር አሁንም ተረጋግታ ፊልሟን እያየች ነው፡፡ እሪሞቱን ከጠረጴዛ ላይ አነሳና ፊልሙን አጠፋው፡፡
ቀና ብላ አየችውና በንዴት የደፈረሱ አይኖቹን እየተመለከተች‹‹ምን ነው?›› ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ ከምታይው የተሻለ ሌላ ልብ አንጠልጣይ ፊልም አብረን እንድናይ ስለፈለኩ ነው፡፡ >> በማለት ከጐኗ ተቀምጦ ላፕቶፑን ለመክፈት ተዘጋጀ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
...ከጊዜ ማህፀን ውስጥ አስደናቂና አሰቃቂ የህይወት ታአምራቶች ተፀንሰው ሲወለዱ ታዝበናል፡፡
የግቢውን በር ዘበኛው እንደከፈተለት መኪናውን ቦታ አስይዞ ለመቆም እንኳን ትዕግስት አልነበረውም፡፡ ሞተሩን አጠፋና እየተንደረደረ ወደ ቤት ገባ፡፡ የውብዳር ብቻዋን መለስተኛ አዳራሽ በሚያክለው ሳሎን ቁጭ ብላ በባለ 36 ኢንች ፍላትስክሪን ሶኒ ቴሌቭዥን ፊልም እየተመለከተች ነው፡፡ ሊያናግራትም አልፈለገም፡፡ዞር ብሎም አላያትም፡፡ ሳሎኑን ሰንጥቆ መኝታ ቤቱ የገባው ላፕቶፑን ፍለጋ ነበር፡፡ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ ከፈተው፡፡ ዲስኩን አውጥቶ ከተተውና እስኪጫወትለት መጠበቅ ጀመረ፡፡ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፡፡
አምስት ሺ ብር ያወጣበት መረጃ ነው፡፡ ላለፉት ሦስት ቀናቶች ሠው ቀጥሮ ሚስቱን ሲያሰልላት ነበር፡፡ ቅጥረኞቹ ባዘዛቸው መሰረት ተከታትለዋታል፡፡ አዋዋሏን ቀርፀው ሙሉ መረጃውን በማስረከብ ብራቸውን ተቀብለው ተሰናብተውታል፡፡ በአንደበታቸው የነገሩት ነገር ባለመኖሩ ምስሉን አይቶ ጥርጣሬውን ከአዕምሮው እስኪፍቅ ቸኩሏል፡፡ሠሎሞን የውብዳርን ለማሠለል የወሰነበት ምክንያት ፀባይዋ፣ አለባበሷ፣አነጋገሯ ጠቅላላ ሁኔታዋ ከበፊቱ በተጋነነ ሁኔታ እየተለወጠ ስለመጣበት ነው፡፡ በእርግጥ መጣላትና መናቆር ከጀመሩ ዓመታት ቢቆጠርም እንደ አለፉት ሦስት ወራቶች ነገሮች መጠን አልፈው አያውቁም፡፡ በዚህም የተነሳ ስድስተኛ የስሜት ህዋሱ እንዲከታተላት ሹክ አለው፡፡
ኮምፒውተሩ መጫወት ጀመረ፡፡ መናፈሻ ቦታ ነው፡፡ ያምራል፡፡ ግቢው በዛፎች እና በአበቦች የደመቀ ነው፡፡ ትክክለኛ ቦታውን መለየት አልቻለም፡፡ የውብዳር የሚያምር ነጭ የፕላስቲክ ወንበር ላይ ተቀምጣለች፡፡ ከጎኗ የወንድ እግር ይታያል፡፡ ፊት ለፊታቸው ለስላሳ መጠጦችና በርገር ተቀምጧል፡፡ፊልሙ ተንቀሳቀሰ፡፡ የወንድየው እጅ ወደ የውብዳር ሰውነት ተንቀሳቀሰ ፡፡ እጁን እጇ ላይ አርጎ ያሻሻታል፡፡ ቀስ በቀስ የሠውዬው አካል እየታየ መጣ፡፡ እስከ ወገብ .. እስከ ደረቱ .. ፊቱ ከመጋለጡ በፊት ግን ነጭ የደንብ ልብስ የለበሰች አስተናጋጅ እፊት ለፊት ተደንቅራ ስክሪኑን ሞላችው፡፡‹‹ብሽቅ›› አለ ሠሎሞን፣የማወቅ ጥሙን በፍጥነት ማርካት ስላልቻለ ተበሳጭቶ፡፡
ከውስን ደቂቃዎች መቋረጥ በኋላ ፊልሙ ዳግም መጫወት ጀመረ፡፡ ሆቴል ውስጥ ነው፡፡ የሁለተኛ ቀን ቀረፃ መሆኑ የሚያስታውቀው የለበሠችው ልብስ የተለየ በመሆኑ ነው፡፡ አለባበሷ ወደ ግማሽ እርቃንነት ያዘነበለ ነው፡፡ አብሯት ያለው ወንድ ማንነት ወዲውኑ ነበር በእስክሪኑ ፊት ብቅ እንዳለ የለየው፡፡ በደንብ ያውቀዋል፡፡ ሹፌሯ ነው፡፡ ተንፈስ አለ፡፡ ማየቱን ግን አላቆመም፡፡ ቀጠለ፡፡ ሁለቱም ፊት ለፊት በማራኪ ብርጭቆ ውስኪ ቀርቧል፡፡ ግራ ገባው፡፡ ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀምጠዋል፡፡ በሳቅ የታጀበ ወሬ ያወራሉ፡፡
ምስሉ ድምፅ አልባ ቢሆንም የከንፈር እንቃስቃሴያቸው ሲታይ፣ በአብዛኛው እሱ ያወራላታል እሷ ትንከታከታለች፡፡ነገሮች
በተመሳሳይ ሁኔታ ለደቂቃዎች ከቀጠሉ በኋላ
አይን የሚስብ ነገር ድንገት ተመለከተ፡፡
የሹፌሩ እጅ በጠረጴዛው ስር አሻግሮ ወደ የውብዳር ጭን እያመራ ነው….፡፡ የለበሰችውን አጭር ጉርድ ቀሚስ ወደ ላይ ገፋ አድርጎ ማሻሸት ጀመረ፡፡ እሷም ግራና ቀኟን ተገላምጣ ከተመለከተች በኋላ ብሩህ የሆነ ፈገግታ ለግሳው፣ ከመቀመጫዋ ወደ ፊት ሸርተት ብላ ተጠጋችለት፡፡ ጣቶቹን ጭኖቿ መሀል ሰነቀራቻውና ማርመስመስ ጀመረ፡፡ ተጋጥመው የነበሩትን እግሮቿን ቀስ በቀስ እያላቀቀች... እየከፈተች መጣች፡፡ መረጋጋት እንዳልቻለች ከፊቷ መቀያየር መረዳት ይቻላል፡፡
ከንፈሮቿ ለንግግር በዝግታ ተነቃነቁ፡፡ የሆነ ነገር መለሰላትና እጆቹን ሰብስቦ አስተናጋጁን ጠራ፡፡ የማይሰማ ነገር እየነገረው እጁን ወደ ኪሱ ሠደደ፡፡እሷ ቀድማ ቦርሳዋ ገባችና
የተወሰኑ የብረ ኖቶችን አውጥታ ቀድማ ለአስተናጋጁ ሠጠችው፡፡
አስተናጋጁ እየተንደረደረ እንግዳ መቀበያ ቢሮ ሲገባ ታየ፡፡ ዳግመኛ እጁን ወደ ጭኖቿ አላከም፡፡ይልቁንም ወደ መጠጡ ሠደደና
ደጋግሞ ይጎነጭ ጀመር፡፡
እሷም ተመሳሳዩን እርምጃ ወሰደች የተወሰነ ደቂቃ ካጠፋ በኋላ አስተናጋጁ ተመልሶ መጣና የማይሰማ ነገር ነገራቸው፡፡ ዝርዝር ብሮች አውጥቶ አስጨበጠውና እጆቿን ይዞ ከተቀመጠችበት አስነሳት፡፡ ወገቧን አቀፈና በጓሮ በር
ይዟት ወጣ። ፊልሙ ተቋረጠ፡፡ ሠሎሞን ላፕቶፑን
ወርውሮ
ከግድግዳ ጋር ሊያላትመው ፈለገ፡፡
ስሜቱን መቆጣጠር እየተሳነው መጥቷል፡፡ በዛ ሠፊ ሆዱ ሙሉ እሳት እየነደደበት ነው፡፡ፊልሙ መጫወቱን ቀጥሎል፡፡ አሁንም ወገቧን እንዳቀፋት ነው፡፡ የሆነ ፎቅ ደረጃ እየወጡ ነው፡፡ በመደዳ የተደረደሩ በሮች ይታያሉ፡፡
የተወሰኑትን ክፍሎች አልፈው ከሄዱ በኋላ ቆሙ፡፡ 2ዐ3 ቁጥር የተለጠፈበት ክፍል አጠገብ ሲደርሱ ከፍቶ ወደ ውስጥ ጎተታት፡፡ እየተፍለቀለቀች ተጎተተችለት፡፡ ቦርሳዋን ወለል ላይ ጥላ ጫማዋን ለማውለቅ ስትጣደፍ ይታያል፡፡ ትእይንቱ ከዚህ በላይ መቀጠል አልቻለም፡፡ በራፉ ከውስጥ ተዘጋ፡፡ጠቅላላ ሠውነቱ ላይ ውሃ እንደከለበሱበት ሠው በላብ ተጠመቀ፡፡ ምን ማድረግ እንዳለበት ማሠብ እንኳን ተሳነው፡፡ መጮኽ... ማበድ... ዕቃ መስበር አሠኘው፡፡ ከሁሉ ነገር በላይ ፊት ለፊት መታለሉ አበገነው፡፡
፨፨፨
የውብዳር ሹፌር ያስፈልገኛል ብላ የጠየቀችው ከአምስት ወር በፊት ነበር፡፡እሷ እራሷ መንዳት እየቻለች ሹፌር ለምን እንዳስፈለጋት ሲጠይቃት፤ ከልብ ድካም በሽታዋ ጋር በተያያዘ ሀኪም ላልተወሠነ ጊዜ መንዳት እንደከለከላት ነበር ያስረዳችው፡፡ ለጉዳዩ ብዙም ትኩረት ሳይሰጠው ፡
‹‹ታዲያ ፈልጊና ቅጠሪያ ምን ችግር አለው፤ ገንዘብ እንደሆነ አለሽ›› ነበር ያላት፡፡
‹‹ገንዘብ ማን ጠየቀህ? የምታውቀው ደህና ሹፌር ካለ እንድታናግርልኝ እንጂ..፡፡››
‹‹እኔ በአንዲት ቀበጥ ወይዘሮ ትእዛዝ በየሱፐር ማርኬትና በየፀጉር መፈሸኛ ቤት ሲንከራተት ለመዋል ትዕግስት ያለው ሹፌር አላውቅም፡፡››
‹‹ባንተ ቤት አሽሙር ተናግረህ ልብህ ውልቅ ብሎል፡፡ በአጭሩ አልችልም ወይም ፍላጎት የለኝም አትልም፡፡ ይብላኝ ላንተ እንጂ ችግር የለውም፡፡ ካገኘሁ አገኘሁ ካላገኘው ደግሞ ለጊዜውም ቢሆን በታክሲ እጠቀማለሁ፡፡ ልጆቹን ወደ ት/ቤት የማመላለሱን ጉዳይ ግን አስብበት›› በማለት ነበር እየተቆናጠረች በቆመበት ጥላው የሄደችው፡፡
ሹፌሩ ተገኝቶ መኪናውን ለመያዝ ግን ሁለት ቀን ብቻ ነበር የፈጀበት፡፡ ከየት አገኘሽው? በስንት ብር ቀጠርሽው? የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አልጠየቃትም፡፡ ሹፌሩ የሃያ አራት ዓመት ገደማ አፍላ ጎረምሳ ነው፡፡ ‹‹ሳምሶን እባላለሁ›› ነበር ያለው በመጀመሪያ ቀን ሲተዋወቀው፡፡ ሚስቱና ልጆቹ ግን ሳሚ እያሉ ነው በቁልምጫ የሚጠሩት፡፡ ስራ እንደጀመረ ሰሞን ነገረ ስራው ሁሉ ባይጥመውም፣ ዋል አደር ሲል ግን ለልጆቹ የሚያደርገውን እንክብካቤና ልጆቹም ምን ያህል በፍቅር እንደተቀበሉት ሲገነዘብ ቅሬታውን ችላ ብሎ ተወው፡፡ይሄዋ ዛሬ ችላ የማለቱን ፍሬ እየተመለከተ ነው፡፡
ላፕቶፑን እንደያዘ እየተንደረደረ ወደ ሳሎን ሄደ፡፡ የውብዳር አሁንም ተረጋግታ ፊልሟን እያየች ነው፡፡ እሪሞቱን ከጠረጴዛ ላይ አነሳና ፊልሙን አጠፋው፡፡
ቀና ብላ አየችውና በንዴት የደፈረሱ አይኖቹን እየተመለከተች‹‹ምን ነው?›› ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ ከምታይው የተሻለ ሌላ ልብ አንጠልጣይ ፊልም አብረን እንድናይ ስለፈለኩ ነው፡፡ >> በማለት ከጐኗ ተቀምጦ ላፕቶፑን ለመክፈት ተዘጋጀ፡፡
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
:
:
ዛሬ ላይ..
ለሊት 11 ሰዓት ተነስተው ቤተክርስቲያን ሄዱ፤ለአባትየው ሰባት ዓመት ፍትሀተ-ፀሎት ከመደረጉ በተጨማሪ የስንዱም የምንኩስና ስርዓት ፀሎት ተደርጎ እማሆይ አፀደማርያ ተብላ ቆብ ደፋች.ይሄ ድርጊት በአብዛኛው ሰው ዘንድ መደነቅን ለጥቂቱ ደግሞ ለሀሜት አሳልፎ ሰጣት…ከቅዳሴ በኋላ ከቤት ተዘጋጅቶ የመጣውን ፀበል ፃዲቅ ሰንበቴ ቤት በመታደም ከተቋደሱ በኋላ ቤት ላለው ዝግጅት ተመለሱ ቀኑን ሙሉ ባለፉት 6 ዓመታት እንደተደረገው ችግረኞችና የኔ ቢጤዎች ሲመላለሱበት ዋሉ…ሳባ በዕለቱ አብዛኛውን ፕሮግራምና ሽር ጉዱን ብትሳተፍም ከአስር ሰዓት በኃላ ግን ደከማት፡፡ ተዝለፍልፋ ሰው መሀል ከመውደቋ በፊት እየተጎተተች ወደመኝታ ቤት ገባችና አልጋ ላይ ወጥታ ተዘረረች..ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰዳት…እንቅልፏ ግን እጅግ ሰቅጣጭ የሆነ ቅዠት የሞላበት ነፍስ አስጨናቂ ነበር…ደግሞ የሚገርመው ሕልሙ እንደ ሆረር ፊልም ከአንዱ አሰቃቂ ትዕይንት ወደሌላ በተሸጋገረ ቁጥር ጭንቀላቷ ውጥርጥር እያለ ሲለጠጥ በትክክል ይታወቃታል…በተለጠጠ ቁጥር ደግሞ ውጥረቱ የሆኑ ነርቮቿን እንደሚበጣጥስ ይሰማትና ከህመሙ ራሷን ለማዳን ከእንቅልፏ ለመንቃት እየጣረች ነው.. አዎ ይታወቃታል..በደንብ ከልቧ እየጣረች ነው…ግን አልቻለችም፡፡ ስንዱ እቃ ለመውሰድ ወደመኝታ ቤት ስትገባ ሳባ በላብ ተደፍቃ ስትወራጭ በማየቷ ወዝውዛ ነበር ከእንቅልፏ ያነቃቻት..
‹‹ወይ ስንድ..ገላገልሺኝ.. እመሰግናለሁ›አለችና ተጠመጠመችባት፡፡
ስንዱም ጭንቅላቷን እያሻሸቻት‹‹ምንድነው ይሄ ሁሉ ላብ? አሞሻል እንዴ አንቺ ልጅ?›ስትል ጠየቀቻት፡
‹‹አይ ሰሞኑን ትንሽ አሞኝ የታዘዘልኝ መድሀኒት ነበር..ስመጣ ግን ረስቼው መጣሁ››
‹‹ታዲያ ለምን ከዚህ አይገዛልሽም?››
‹‹አይ እንዲህ በቀላሉ የሚገኝ አይነት አይደለም..ማዘዣው ስለሌለኝ አይሸጡልኝም፡፡ግዴለሽም አሁን ትንሽ ስለተኛሁበት ይሻለኛል..ወደ እንግዶችሽ ተመለሺ››
‹‹እሺ በቃ መለስ መለስ እያልኩ አይሻለሁ..››ብላ ግንባሯን ሳመችና በራፉን ዘግታላት ወጥታ ሔደች፡፡
ሳባም መልሶ እንቅልፍ እንዳይወስዳትና ወደተመሳሳይ ቅዠት ገብታ ስቃይ ውስጥ ላለመግባት ስትል ወደሀሳብ ውስጥ ገባች ወደ ትናንቷ ተመለሰች፡፡ትዝ ይላታል የዛን ሰሞን አሰላ ሄዳ ቤተሰቦቿን ጠይቃ ከተመለሰች በኋላ እና አባቷ ደብቆ ሻንጣዋ ውስጥ ያስቀመጠላትን 3ሺብር ካገኘች በኋላ ምንም ሰላም ማግኘት አልቻለችም ነበር፡፡ ቀንና ለሊት ሕይወቷን እንዴት ማስተካከል እንደምትችልና ከቤተሰቧ ድጎማ እራሷን አላቃ በተራዋ ለቤተሰቦቿ ተገቢውን ድጋፍ እንዴት ልታደርግ እንደምትችል ማሰብ ነበር ቋሚ ስራዋ፡፡ ብዙም ሳይቆይ ግን ተዓምር ተከሰተ፡፡፡:
ትዝ ይላታል ማክሰኞ ቀን ነው፡፡ ስራ ገበታዋ ላይ ሆና በተለመደ መልኩ ባለጉዳዬችን እያስተናገደች ሳለ ረፋድ ላይ አንድ እጅግ ዘመናዊ ጥራት ያላቸው ብራንድ ልብሶች የለበሰች፤ውድ የሆኑ አብረቅራቂ ጌጣጌጦችን ጆሮዎቿና እጆቿ ላይ የደረደረች ሴት ወደ ቢሮዋ የገባችው፡፡ልክ እንዳየቻት ነው ልቧ የደነገጠላት..በሁለመናዋ ነው የቀናችባት….አየሩን ሞልቶ ወደ አፍንጫዋ ሰርጎ በገባው ውድ ሽቶዋ ሳይቀር ቀናችባት፡፡እናም ሳታስበው ከወትሮ በተለየ አይነት ፈግታና ቅልጥፍና ሴትዬዋን ማስተናገድ ጀመረች፡፡ እሷ የምትጨርሳቸውን ስራዎች ብቻ ሳይሆን በሌሎች ቢሮዎች የሚሰሩ እና የሚፈረሙ ፊርማዎችን ሳይቀር ሴትዬዋን የራሷ ቢሮ አስቀምጣ እሷ (ልክ ጉቦ ይሰጥሀል እንደተባለ ኤክስፐርት) ተዟዙራ አስጨረሰችላትና ሰጠቻት፡፡
ከዛም ሴትዬዋ..ወረቀቷን ተቀብላ ትሄዳለች ብላ ስትጠብቅ ተመቻችታ ፊት ለፊቷ ተቀመጠችና….‹‹ስሜን መቼስ ከሰነዱ አንብበሻል…ትብለጥ እባለለሁ…››
‹‹እኔ ደግሞ ሳባ››ስትል የራሷንም ነገረቻት፡፡
‹‹ሳባ ዋው…ስምሽም እንደመልክሽያምራል››አለቻት፡፡የሴትዬዋ ንግግር ቀጥታ ልቧ ላይ አርፎ ነበር ቅልጥ ያደረጋት፡፡ አንድ ጎረምሳ ወንድ እንኳን እንደዛ አይነት አስተያየት ቢሰጣት የዛን አይነት ስሜት በውስጧ አያጭርባትም፡
‹‹አመሰግናለሁ….›› አለች ሌላ ምትለው ነገር ስለጠፋት፡፡
ሴትዬዋ ቀጠለች‹‹ስራ እንዴት ነው?››
‹‹ያው እንደምታይው ነው…ምንም አይልም››
‹‹ምንም አይልም ነው ወይስ ጥሩ ነው ነው?›
‹‹አይ ምንም አይልም…ጥሩ የሚባል ስራ እንዲህ በቀላሉ ይኖራል ብለሽ ነው?›› አለቻት ሰሞኑን ስላለችበት ብሶት እያሰላሰለች፡
‹‹እንደ አንቺ ቆንጆ፤መለሎ ቁመና የተስተካከለ የሰውነት ቅርፅ ያላትና በዛ ላይ የተማረች ሴትማ በጣም ጥሩ የተባለ ስራ ሊኖራት የግድ ነው…››አለችና እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰዳ የቢዝነስ ካርዷን አወጣችና ጠረጴዛዋ ላይ እያስቀመጠችላት
‹‹ይሄውልሽ ሳባ ለምን እንደሆነ አላውቅም ወድጄሻለሁ ምን አልባት ጥሩ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ በምትፈልጊበት ቀን ደውይልኝ….በይ ቻው ለመስተንግዶሽ አመሰግናለሁ፡፡››ብላ ጉንጯን ሳመችና ቢሮዋን ለቃ ወጣች፡፡ ሳባም በተቀመጠችበት መቀመጫ ደንዝዛ በፈዘዙ አይኖቿ ከኋላዋ ተከተለቻት ሴትዬዋ እየተሞናደለች ቢሮውን ለቃ ስትወጣ በራፍ ላይ ሁለት ወጠምሻና ባለጡንቻ ወጣቶች እየጠበቋት.ነበር….መሀከል አስገብተዋት ይዘዋት ሄዱ…፡፡
‹‹ይህቺ ባለስልጣን ነች ወይስ የባለስልጣን ሚስት?› ስትል ራሷን ጠየቀች….ብንን እንደማለት አለችና ትታላት የሄደችውን ቢዝነስ ካርድ አነሳችና…አየችው..
ትብለጥ ግዛው፡፡
‹‹ቤርሙዳ ማሳጅ ቤት›› ይላል፡፡
‹‹እንዴ ባለማሳጅ ቤት ነች ግን አስመጪና ላኪ ነው የምትመስለው›› ስትል የስራዋ አይነት ከግምቷ ውጭ ሰለመሆኑ አብሰለሰለች፡፡ሌላ ባለጉዳይ ገባባት፡፡ሳትወድ.በግዷ.ሀሳቡን ለጊዜው በልቧ ሸሸገችውና ወደስራዋ ተመለሰች፡፡ማታ ቤት ገብታም ስለሴትዬዋ ማሰቧን አላቋረጠችም ነበር፡፡ ወንድ ብትሆን "ፍቅር ያዘኝ እንዴ?ብላ ራሷን መጠራጠር ትጀምር ነበር...ሴትዬዋ የማሳጅ ቤት ባለቤት መሆኗን ከቢዝነስ ካርዷ ብትረዳም ‹‹የፈለገችኝ ለሌላ ስራ ቢሆንስ?››የሚል ሀሳብ በአእምሮዋ ብልጭ አለባት። እንደምንም ራሷን ተቆጣጠረችና አራት ቀን በመቆየት በአምስተኛው ቀን ደወለችላት፡፡
💫ይቀጥላል💫
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
:
:
ዛሬ ላይ..
ለሊት 11 ሰዓት ተነስተው ቤተክርስቲያን ሄዱ፤ለአባትየው ሰባት ዓመት ፍትሀተ-ፀሎት ከመደረጉ በተጨማሪ የስንዱም የምንኩስና ስርዓት ፀሎት ተደርጎ እማሆይ አፀደማርያ ተብላ ቆብ ደፋች.ይሄ ድርጊት በአብዛኛው ሰው ዘንድ መደነቅን ለጥቂቱ ደግሞ ለሀሜት አሳልፎ ሰጣት…ከቅዳሴ በኋላ ከቤት ተዘጋጅቶ የመጣውን ፀበል ፃዲቅ ሰንበቴ ቤት በመታደም ከተቋደሱ በኋላ ቤት ላለው ዝግጅት ተመለሱ ቀኑን ሙሉ ባለፉት 6 ዓመታት እንደተደረገው ችግረኞችና የኔ ቢጤዎች ሲመላለሱበት ዋሉ…ሳባ በዕለቱ አብዛኛውን ፕሮግራምና ሽር ጉዱን ብትሳተፍም ከአስር ሰዓት በኃላ ግን ደከማት፡፡ ተዝለፍልፋ ሰው መሀል ከመውደቋ በፊት እየተጎተተች ወደመኝታ ቤት ገባችና አልጋ ላይ ወጥታ ተዘረረች..ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰዳት…እንቅልፏ ግን እጅግ ሰቅጣጭ የሆነ ቅዠት የሞላበት ነፍስ አስጨናቂ ነበር…ደግሞ የሚገርመው ሕልሙ እንደ ሆረር ፊልም ከአንዱ አሰቃቂ ትዕይንት ወደሌላ በተሸጋገረ ቁጥር ጭንቀላቷ ውጥርጥር እያለ ሲለጠጥ በትክክል ይታወቃታል…በተለጠጠ ቁጥር ደግሞ ውጥረቱ የሆኑ ነርቮቿን እንደሚበጣጥስ ይሰማትና ከህመሙ ራሷን ለማዳን ከእንቅልፏ ለመንቃት እየጣረች ነው.. አዎ ይታወቃታል..በደንብ ከልቧ እየጣረች ነው…ግን አልቻለችም፡፡ ስንዱ እቃ ለመውሰድ ወደመኝታ ቤት ስትገባ ሳባ በላብ ተደፍቃ ስትወራጭ በማየቷ ወዝውዛ ነበር ከእንቅልፏ ያነቃቻት..
‹‹ወይ ስንድ..ገላገልሺኝ.. እመሰግናለሁ›አለችና ተጠመጠመችባት፡፡
ስንዱም ጭንቅላቷን እያሻሸቻት‹‹ምንድነው ይሄ ሁሉ ላብ? አሞሻል እንዴ አንቺ ልጅ?›ስትል ጠየቀቻት፡
‹‹አይ ሰሞኑን ትንሽ አሞኝ የታዘዘልኝ መድሀኒት ነበር..ስመጣ ግን ረስቼው መጣሁ››
‹‹ታዲያ ለምን ከዚህ አይገዛልሽም?››
‹‹አይ እንዲህ በቀላሉ የሚገኝ አይነት አይደለም..ማዘዣው ስለሌለኝ አይሸጡልኝም፡፡ግዴለሽም አሁን ትንሽ ስለተኛሁበት ይሻለኛል..ወደ እንግዶችሽ ተመለሺ››
‹‹እሺ በቃ መለስ መለስ እያልኩ አይሻለሁ..››ብላ ግንባሯን ሳመችና በራፉን ዘግታላት ወጥታ ሔደች፡፡
ሳባም መልሶ እንቅልፍ እንዳይወስዳትና ወደተመሳሳይ ቅዠት ገብታ ስቃይ ውስጥ ላለመግባት ስትል ወደሀሳብ ውስጥ ገባች ወደ ትናንቷ ተመለሰች፡፡ትዝ ይላታል የዛን ሰሞን አሰላ ሄዳ ቤተሰቦቿን ጠይቃ ከተመለሰች በኋላ እና አባቷ ደብቆ ሻንጣዋ ውስጥ ያስቀመጠላትን 3ሺብር ካገኘች በኋላ ምንም ሰላም ማግኘት አልቻለችም ነበር፡፡ ቀንና ለሊት ሕይወቷን እንዴት ማስተካከል እንደምትችልና ከቤተሰቧ ድጎማ እራሷን አላቃ በተራዋ ለቤተሰቦቿ ተገቢውን ድጋፍ እንዴት ልታደርግ እንደምትችል ማሰብ ነበር ቋሚ ስራዋ፡፡ ብዙም ሳይቆይ ግን ተዓምር ተከሰተ፡፡፡:
ትዝ ይላታል ማክሰኞ ቀን ነው፡፡ ስራ ገበታዋ ላይ ሆና በተለመደ መልኩ ባለጉዳዬችን እያስተናገደች ሳለ ረፋድ ላይ አንድ እጅግ ዘመናዊ ጥራት ያላቸው ብራንድ ልብሶች የለበሰች፤ውድ የሆኑ አብረቅራቂ ጌጣጌጦችን ጆሮዎቿና እጆቿ ላይ የደረደረች ሴት ወደ ቢሮዋ የገባችው፡፡ልክ እንዳየቻት ነው ልቧ የደነገጠላት..በሁለመናዋ ነው የቀናችባት….አየሩን ሞልቶ ወደ አፍንጫዋ ሰርጎ በገባው ውድ ሽቶዋ ሳይቀር ቀናችባት፡፡እናም ሳታስበው ከወትሮ በተለየ አይነት ፈግታና ቅልጥፍና ሴትዬዋን ማስተናገድ ጀመረች፡፡ እሷ የምትጨርሳቸውን ስራዎች ብቻ ሳይሆን በሌሎች ቢሮዎች የሚሰሩ እና የሚፈረሙ ፊርማዎችን ሳይቀር ሴትዬዋን የራሷ ቢሮ አስቀምጣ እሷ (ልክ ጉቦ ይሰጥሀል እንደተባለ ኤክስፐርት) ተዟዙራ አስጨረሰችላትና ሰጠቻት፡፡
ከዛም ሴትዬዋ..ወረቀቷን ተቀብላ ትሄዳለች ብላ ስትጠብቅ ተመቻችታ ፊት ለፊቷ ተቀመጠችና….‹‹ስሜን መቼስ ከሰነዱ አንብበሻል…ትብለጥ እባለለሁ…››
‹‹እኔ ደግሞ ሳባ››ስትል የራሷንም ነገረቻት፡፡
‹‹ሳባ ዋው…ስምሽም እንደመልክሽያምራል››አለቻት፡፡የሴትዬዋ ንግግር ቀጥታ ልቧ ላይ አርፎ ነበር ቅልጥ ያደረጋት፡፡ አንድ ጎረምሳ ወንድ እንኳን እንደዛ አይነት አስተያየት ቢሰጣት የዛን አይነት ስሜት በውስጧ አያጭርባትም፡
‹‹አመሰግናለሁ….›› አለች ሌላ ምትለው ነገር ስለጠፋት፡፡
ሴትዬዋ ቀጠለች‹‹ስራ እንዴት ነው?››
‹‹ያው እንደምታይው ነው…ምንም አይልም››
‹‹ምንም አይልም ነው ወይስ ጥሩ ነው ነው?›
‹‹አይ ምንም አይልም…ጥሩ የሚባል ስራ እንዲህ በቀላሉ ይኖራል ብለሽ ነው?›› አለቻት ሰሞኑን ስላለችበት ብሶት እያሰላሰለች፡
‹‹እንደ አንቺ ቆንጆ፤መለሎ ቁመና የተስተካከለ የሰውነት ቅርፅ ያላትና በዛ ላይ የተማረች ሴትማ በጣም ጥሩ የተባለ ስራ ሊኖራት የግድ ነው…››አለችና እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰዳ የቢዝነስ ካርዷን አወጣችና ጠረጴዛዋ ላይ እያስቀመጠችላት
‹‹ይሄውልሽ ሳባ ለምን እንደሆነ አላውቅም ወድጄሻለሁ ምን አልባት ጥሩ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ በምትፈልጊበት ቀን ደውይልኝ….በይ ቻው ለመስተንግዶሽ አመሰግናለሁ፡፡››ብላ ጉንጯን ሳመችና ቢሮዋን ለቃ ወጣች፡፡ ሳባም በተቀመጠችበት መቀመጫ ደንዝዛ በፈዘዙ አይኖቿ ከኋላዋ ተከተለቻት ሴትዬዋ እየተሞናደለች ቢሮውን ለቃ ስትወጣ በራፍ ላይ ሁለት ወጠምሻና ባለጡንቻ ወጣቶች እየጠበቋት.ነበር….መሀከል አስገብተዋት ይዘዋት ሄዱ…፡፡
‹‹ይህቺ ባለስልጣን ነች ወይስ የባለስልጣን ሚስት?› ስትል ራሷን ጠየቀች….ብንን እንደማለት አለችና ትታላት የሄደችውን ቢዝነስ ካርድ አነሳችና…አየችው..
ትብለጥ ግዛው፡፡
‹‹ቤርሙዳ ማሳጅ ቤት›› ይላል፡፡
‹‹እንዴ ባለማሳጅ ቤት ነች ግን አስመጪና ላኪ ነው የምትመስለው›› ስትል የስራዋ አይነት ከግምቷ ውጭ ሰለመሆኑ አብሰለሰለች፡፡ሌላ ባለጉዳይ ገባባት፡፡ሳትወድ.በግዷ.ሀሳቡን ለጊዜው በልቧ ሸሸገችውና ወደስራዋ ተመለሰች፡፡ማታ ቤት ገብታም ስለሴትዬዋ ማሰቧን አላቋረጠችም ነበር፡፡ ወንድ ብትሆን "ፍቅር ያዘኝ እንዴ?ብላ ራሷን መጠራጠር ትጀምር ነበር...ሴትዬዋ የማሳጅ ቤት ባለቤት መሆኗን ከቢዝነስ ካርዷ ብትረዳም ‹‹የፈለገችኝ ለሌላ ስራ ቢሆንስ?››የሚል ሀሳብ በአእምሮዋ ብልጭ አለባት። እንደምንም ራሷን ተቆጣጠረችና አራት ቀን በመቆየት በአምስተኛው ቀን ደወለችላት፡፡
💫ይቀጥላል💫
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከዛ በኃላ ኑሀሚ በመገረም እንደተዋጠች ፊቷን አዙራ ወደወንድሟ ነበር የተመለሰችው፡፡ እንደደረሰች ጆንያውንና አሮጌ ብርድልብሱን ገለጠችና ወንድሟ እቅፍ ውስጥ ገባች፡፡
‹‹ምነው አኮረፍሽ?››
‹‹አረ ይህቺ ደነዝ ነች…ጭራሽ ታሾፋለች፡፡››
‹‹ይገልሻል አላልሻትም?››
‹‹አይገባትም አልኩህ እኮ …የጨለለች ሳትሆን አትቀርም ፡፡››
ወዲያው ንግግራቸውን ሳያገባድዱ ነበር የቾንቤ ድምፅ የተሰማው .. እያጓራና እየለፈለፈ ወደእነሱ እየቀረበ ነበር…‹‹ተሸፋፈኚ ..ተሸፋፈኚ….››ናኦል እህቱን አስጠነቀቀ፡፡ሁለቱም ተሸፋፈኑና አይኖቻቸውን በብርድልብሱ ቀዳዳ አጨንቁረው የሚሆነውን ለመመልከት ዝግጁ ሆኑ፡፡እንደጠበቁት ቾንቤ እየለፈለፈና እየፎከረ ቀጥታ ወደልጅቷ ነበር የሄደው፡፡ዘና ብላ ከተቀመጠችበት ነቅነቅ ሳትል እየጠበቀችው ነበር፡፡
‹‹ወንድሜ አለቀላት..ስታሳዝን››ኑሀሚ በቀጣይ የሚሆነውን እየገመተች ተሸማቀቀች፡፡
ቾንቤ ደረሰባትና ዘፍ ብሎ ስሯ ቁጭ አለ፡፡ያ ሁሉ ሲሆን ከልጅቷ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እየታያቸው አልነበረም ፡፡
‹‹ምንም እየተንቀሳቀሰች እኮ አይደለም፡፡››
‹‹አዎ መሞት እንደምትፈልግ ነግራኛለች…እንዲገድላት ነው የምትፈልገው፡፡›› ከልጅቷ ጋር ባደረገችው ንግግር የገባት የመሰላትን ለወንድሟ አብራራችለት፡፡
ቾምቤ ሲያቅፋት ተመለከቱ…ወደኃላ ሊያስተኛት እየሞከረ ነበር፡፡ከዛ እጇን አዙራ ስታቅፈው አዩ…..‹‹እንዴ ልጅቷ እራሷ መከካት ፈልጋለች መሰለኝ?›› ናኦል ነበር ተናጋሪው፡፡
ቀስ ብላ ወደኃላ አስተኛችውና እሷ ተነስታ ቆመች፡፡ከዛ ልብሷን ረገፍ ረገፍ አደረገችና ስሯ የነበረውን አንድ ጥቁር ፔስታል ይዛ ሁለት ሜትር ያህል ከእሱ ራቅ አለችና ተቀመጠች..ቾምቤ እንደተዘረረ ነው..እየተንቀሳቀሰ አይደለም፡፡››
‹‹ወይኔ አይንቀሳቀስም እኮ፡፡››
‹‹ምን አደረገችው?››
‹‹እኔ እንጃ…ሁለቱም ከተሸፋፈኑበት ገልጠው ወጡ፡፡አስር ደቂቃ ያህል ጠበቁ….፡፡ምንም የተለየ ነገር እየታያቸው አልነበረም…፡፡እንደውም ልጅቷ ከፔስታሏ ውስጥ ሻርፕ ነገር አውጥታ ፊቷን ተሸፋፈነችና ሸርተት ብላ ግንቡን ተደግፋ እንደመተኛት አለች፡፡
‹‹እንዴ ገደላት ስንል ገደለችው እንዴ….?››እሱ የለበሰውን ከላዩ ገፎ ተነሳ
‹‹ወዴት ነው?››ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹ …ሄጄ ላጣራ?›››
‹‹ቆይ አብረን እንሂድ ፡፡››አለችና እሷም ተነሳች፡፡ፈራ ተባ እያሉ ተጠጉ፡፡ ደረሱ…. ቾምቤ እጥፍጥፍ ብሎ እንደተኛ ነበር፡፡
‹‹እ ጩጬዎቹ ምንነው?››
‹‹ደየመብሽ እንዴ?››ናኦል ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹ጎንበስ ብለህ እየው…..እኔ እንዲተኛ ብቻ ነው ያደረኩት፡፡ሞቶም ከሆነ የእኔ የእጅ የለበትም፡፡››
‹‹ካራቲስት ነገር ነሽ እንዴ..?እንዴት አድርገሽ ቆለፍሽው?››
ናኦል ጎንበስ አለና ትንፋሹን አዳመጠው፡፡እውነትም አልሞተም፡፡ ትንፋሹ በደንብ ይሰማል፡፡
‹‹አይ ሰላም ነው፡፡››
‹‹ኑ እስቲ ከጎኔ ተቀመጡ፡፡››
ሁለቱ ታዳጊዎች እርስበርስ ተያዩ፡፡ የዚህችን እንግዳ ሴት ግብዣ እንቀበል ወይስ ይቅርብን ሚለውን በአይን እየተነጋገሩ ይመስል ነበር፡፡ከዛ እንደተግባባ ሰው ወደእሷ ቀረቡና እሱ በቀኟ እሷ ደግሞ በግራዋ በኩል ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ቆያችሁ…ማለቴ በርንዳ ላይ?››ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹አዎ አንድ አመት ሊሞላን ነው፡፡››
‹‹ታዲያ አይተናኮሏችሁም…በተለይ አንቺን፡፡››
‹‹አይ እንደመጣን ሰሞን ያስቸግሩን ነበር..ግን እዛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሰራ ፓሊስ አባታችንን በደንብ ያውቀው ነበር..እና እዚህ ሰፈር ላሉት ጉልቤዎች በጠቅላላ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡አንድ ሰው እኛን ቢያጠቃ ሁሉንም እንደሚያጠፋችው ስለነገራቸው አይነኩንም፡፡››በሰላም እየኖሩ ያሉበትን ምክንያት በግልፅ አብራሩላት፡፡
‹‹ለጊዜው ጥሩ ነው..ግን እዚህ ጎዳና ላይ እስከኖራችሁ ድረስ በሌላ ሰው ላይ ተማምናችሁ እስከመጨረሻው ከጥቃት ተጠብቃችሁ መኖር አትችሉም፡፡ያላችሁት ፖሊስ አዛዥ የመንግስት ቅጥረኛ ነው፡፡መንግስት ደግሞ ነገ ተነስቶ ሌላ ወረዳ ወይም ሌላ ከተማ ሊመድበው ይችላል፡፡የዛን ጊዜስ ምን ትሆናላችሁ?››በውድቅት ለሊት ቀን እንኳን ቢሆን መመለስ ሚከብድ ጥያቄ ነበር የጠየቀቻቸው፡፡፡
‹‹እውነትሽን ነው..ይሄ ጉዳይ ሁሌ ያስጨንቀኛል….ለእኔ ሳይሆን ለእህቴ?››የሚል መልስ እንደሰጣት ያስታውሳል፡፡
‹‹እንዴ እንዲህ እንደምታስብ እኮ አንድም ቀን ነግረኸኝ አታውቅም…?›› ኑሀሚ በጭለማው ውስጥ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ብዬሽ እንድትፈሪ አደርጋለሁ?››
ልጅቷ ቦርሳዋን በረበረችና ትንሽ የመጠጥ ብልቃጥ በማውጣት ክዳኑን አሽከርክራ ከፈተችና ተጎነጨችለትና መልሳ በመክደን ከፊት ለፊቷ አስቀመጠች፡፡
‹‹የት ነበርሽ..?ማለቴ እዚህ ሰፈር እንዴት ልትመጪ ቻልሽ?››
‹‹እንዲሁ በዚህ ሳልፍ ሰፈሩ ደስ አለኝና እዚሁ አረፍ አልኩ፡፡››
‹‹እና ነገ ትሄጂያለሽ ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ… ሂጂ ሂጂ ካለኝ እሄዳለሁ፡፡››
ናኦል‹‹ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡እንደዛ ያላት ልጅቷ በእድሜ በጣም ታላቁ ብትሆንም ገና እንዳያት በጣም ስለወደዳት ነበር…የዛን ጊዜ ስለእሷ የተሰማው ስሜት ዛሬም ድረስ በልቡ ላይ ተቋጥሮ እንደቆረቆረው ነው፡፡
ዞር ብላ አየችውና እጆቾን ዘርግታ ፀጉሩን እያሻሸች‹‹ጎረምሳው…ተከየፍክብኝ እንዴ?››ነበር ያለችው፡፡
እንደማፈር አለና …አቀርቅሮ ዝም አላት፡፡በወቅቱ ብዙ ነገር ሊመልስላት ፈልጎ ነበር፡፡ግን ከንፈሮቹ ተነቃንቀው ቃላት ከአንደበቱ ማውጣት አልቻሉም፡፡
‹‹አይዞኝ ስቀልድ ነው፡፡ለማንኛውም አሁን ሂዱና ተኙ፡፡.ነገ እናወራለን፡፡››
‹‹እሺ›› አሉና ሁላቱም ከግራና ከቀኞ ተነስተው ባዶ መሬት ላይ ዘና ብሎ በመዘረጋጋት ተኝቶ እያንኳራፋ ያለውን ቾንቤን በጎሪጥ እያዩ በስሩ አልፈው ወደመኝታቸው ሄዱ፡፡ኑሀሚና ናኦል ጥዋት ተነስተው አካባቢውን ሲቃኙ የለሊቷ ልጅ ተነስታ ልክ እንደደላው የቤት ልጅ ስፖርት እየሰራች ነበር ያገኞት፡፡…ሳንቾ በአካባቢው የለም፡፡ሌሎች ጓደኞቻቸው የተወሰኑት ተኝታዋል…የተቀሩትም ወደሚሄድበት ሄደዋል፡፡ለብሳው ያደሩትን አሮጌ ብርድልብስ እና ጆንያ ከስር የሚያነጥፉትን ካርቶን ስብስበውና አጣጥፈው ወደጥግ በማድረግ ዘወትር እንደሚያደርጉት በላዩ ላይ ድንጋይ ጭኑበት እና ወደልጅቷ ሄዱ ፡፡
‹‹እ ጩጬዎች ..ተነሳችሁ፡፡››በሚል ጥያቄ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡
‹‹አዎ…ቡሌ ፍለጋ ልንሄድ ነው… ትመጪያለሽ?››
‹‹አዎ…››አለችና እስፖርቷን አቋርጣ ..ፔስታሏን ያዘችና ተከተለቻቸው፡፡
‹‹እ የት ነው ምንበላው?
ሁለቱም አፍጥጠው አዮት‹‹እንዴ ገና ሆቴል ሄደን ተመላሽ ጠይቀን ነዋ››ኑሀሚ ነበረች በመኮሳተር የመለሰችላት፡፡
‹‹አይ ብር አለኝ ..ለምን ገዝተን አንበላም…፡፡››
ሁለቱም በደስታ ፈገግ አሉ…‹‹ስንት አለሽ..?››ናኦል ነበር ጠያቂው፡፡
‹‹ጅንስ ሱሪ ኪሷ ውስጥ እጇን ሰደደችና ሁለት መቶ ብር መዛ አወጣች…››
‹‹አይበቃም…››
‹‹አረ ይበቃል..ነይ ዝናሽ ጋር እንሂድ፡፡››
‹‹ዝናሽ ማነች…?››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከዛ በኃላ ኑሀሚ በመገረም እንደተዋጠች ፊቷን አዙራ ወደወንድሟ ነበር የተመለሰችው፡፡ እንደደረሰች ጆንያውንና አሮጌ ብርድልብሱን ገለጠችና ወንድሟ እቅፍ ውስጥ ገባች፡፡
‹‹ምነው አኮረፍሽ?››
‹‹አረ ይህቺ ደነዝ ነች…ጭራሽ ታሾፋለች፡፡››
‹‹ይገልሻል አላልሻትም?››
‹‹አይገባትም አልኩህ እኮ …የጨለለች ሳትሆን አትቀርም ፡፡››
ወዲያው ንግግራቸውን ሳያገባድዱ ነበር የቾንቤ ድምፅ የተሰማው .. እያጓራና እየለፈለፈ ወደእነሱ እየቀረበ ነበር…‹‹ተሸፋፈኚ ..ተሸፋፈኚ….››ናኦል እህቱን አስጠነቀቀ፡፡ሁለቱም ተሸፋፈኑና አይኖቻቸውን በብርድልብሱ ቀዳዳ አጨንቁረው የሚሆነውን ለመመልከት ዝግጁ ሆኑ፡፡እንደጠበቁት ቾንቤ እየለፈለፈና እየፎከረ ቀጥታ ወደልጅቷ ነበር የሄደው፡፡ዘና ብላ ከተቀመጠችበት ነቅነቅ ሳትል እየጠበቀችው ነበር፡፡
‹‹ወንድሜ አለቀላት..ስታሳዝን››ኑሀሚ በቀጣይ የሚሆነውን እየገመተች ተሸማቀቀች፡፡
ቾንቤ ደረሰባትና ዘፍ ብሎ ስሯ ቁጭ አለ፡፡ያ ሁሉ ሲሆን ከልጅቷ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እየታያቸው አልነበረም ፡፡
‹‹ምንም እየተንቀሳቀሰች እኮ አይደለም፡፡››
‹‹አዎ መሞት እንደምትፈልግ ነግራኛለች…እንዲገድላት ነው የምትፈልገው፡፡›› ከልጅቷ ጋር ባደረገችው ንግግር የገባት የመሰላትን ለወንድሟ አብራራችለት፡፡
ቾምቤ ሲያቅፋት ተመለከቱ…ወደኃላ ሊያስተኛት እየሞከረ ነበር፡፡ከዛ እጇን አዙራ ስታቅፈው አዩ…..‹‹እንዴ ልጅቷ እራሷ መከካት ፈልጋለች መሰለኝ?›› ናኦል ነበር ተናጋሪው፡፡
ቀስ ብላ ወደኃላ አስተኛችውና እሷ ተነስታ ቆመች፡፡ከዛ ልብሷን ረገፍ ረገፍ አደረገችና ስሯ የነበረውን አንድ ጥቁር ፔስታል ይዛ ሁለት ሜትር ያህል ከእሱ ራቅ አለችና ተቀመጠች..ቾምቤ እንደተዘረረ ነው..እየተንቀሳቀሰ አይደለም፡፡››
‹‹ወይኔ አይንቀሳቀስም እኮ፡፡››
‹‹ምን አደረገችው?››
‹‹እኔ እንጃ…ሁለቱም ከተሸፋፈኑበት ገልጠው ወጡ፡፡አስር ደቂቃ ያህል ጠበቁ….፡፡ምንም የተለየ ነገር እየታያቸው አልነበረም…፡፡እንደውም ልጅቷ ከፔስታሏ ውስጥ ሻርፕ ነገር አውጥታ ፊቷን ተሸፋፈነችና ሸርተት ብላ ግንቡን ተደግፋ እንደመተኛት አለች፡፡
‹‹እንዴ ገደላት ስንል ገደለችው እንዴ….?››እሱ የለበሰውን ከላዩ ገፎ ተነሳ
‹‹ወዴት ነው?››ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹ …ሄጄ ላጣራ?›››
‹‹ቆይ አብረን እንሂድ ፡፡››አለችና እሷም ተነሳች፡፡ፈራ ተባ እያሉ ተጠጉ፡፡ ደረሱ…. ቾምቤ እጥፍጥፍ ብሎ እንደተኛ ነበር፡፡
‹‹እ ጩጬዎቹ ምንነው?››
‹‹ደየመብሽ እንዴ?››ናኦል ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹ጎንበስ ብለህ እየው…..እኔ እንዲተኛ ብቻ ነው ያደረኩት፡፡ሞቶም ከሆነ የእኔ የእጅ የለበትም፡፡››
‹‹ካራቲስት ነገር ነሽ እንዴ..?እንዴት አድርገሽ ቆለፍሽው?››
ናኦል ጎንበስ አለና ትንፋሹን አዳመጠው፡፡እውነትም አልሞተም፡፡ ትንፋሹ በደንብ ይሰማል፡፡
‹‹አይ ሰላም ነው፡፡››
‹‹ኑ እስቲ ከጎኔ ተቀመጡ፡፡››
ሁለቱ ታዳጊዎች እርስበርስ ተያዩ፡፡ የዚህችን እንግዳ ሴት ግብዣ እንቀበል ወይስ ይቅርብን ሚለውን በአይን እየተነጋገሩ ይመስል ነበር፡፡ከዛ እንደተግባባ ሰው ወደእሷ ቀረቡና እሱ በቀኟ እሷ ደግሞ በግራዋ በኩል ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ቆያችሁ…ማለቴ በርንዳ ላይ?››ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹አዎ አንድ አመት ሊሞላን ነው፡፡››
‹‹ታዲያ አይተናኮሏችሁም…በተለይ አንቺን፡፡››
‹‹አይ እንደመጣን ሰሞን ያስቸግሩን ነበር..ግን እዛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሰራ ፓሊስ አባታችንን በደንብ ያውቀው ነበር..እና እዚህ ሰፈር ላሉት ጉልቤዎች በጠቅላላ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡አንድ ሰው እኛን ቢያጠቃ ሁሉንም እንደሚያጠፋችው ስለነገራቸው አይነኩንም፡፡››በሰላም እየኖሩ ያሉበትን ምክንያት በግልፅ አብራሩላት፡፡
‹‹ለጊዜው ጥሩ ነው..ግን እዚህ ጎዳና ላይ እስከኖራችሁ ድረስ በሌላ ሰው ላይ ተማምናችሁ እስከመጨረሻው ከጥቃት ተጠብቃችሁ መኖር አትችሉም፡፡ያላችሁት ፖሊስ አዛዥ የመንግስት ቅጥረኛ ነው፡፡መንግስት ደግሞ ነገ ተነስቶ ሌላ ወረዳ ወይም ሌላ ከተማ ሊመድበው ይችላል፡፡የዛን ጊዜስ ምን ትሆናላችሁ?››በውድቅት ለሊት ቀን እንኳን ቢሆን መመለስ ሚከብድ ጥያቄ ነበር የጠየቀቻቸው፡፡፡
‹‹እውነትሽን ነው..ይሄ ጉዳይ ሁሌ ያስጨንቀኛል….ለእኔ ሳይሆን ለእህቴ?››የሚል መልስ እንደሰጣት ያስታውሳል፡፡
‹‹እንዴ እንዲህ እንደምታስብ እኮ አንድም ቀን ነግረኸኝ አታውቅም…?›› ኑሀሚ በጭለማው ውስጥ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ብዬሽ እንድትፈሪ አደርጋለሁ?››
ልጅቷ ቦርሳዋን በረበረችና ትንሽ የመጠጥ ብልቃጥ በማውጣት ክዳኑን አሽከርክራ ከፈተችና ተጎነጨችለትና መልሳ በመክደን ከፊት ለፊቷ አስቀመጠች፡፡
‹‹የት ነበርሽ..?ማለቴ እዚህ ሰፈር እንዴት ልትመጪ ቻልሽ?››
‹‹እንዲሁ በዚህ ሳልፍ ሰፈሩ ደስ አለኝና እዚሁ አረፍ አልኩ፡፡››
‹‹እና ነገ ትሄጂያለሽ ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ… ሂጂ ሂጂ ካለኝ እሄዳለሁ፡፡››
ናኦል‹‹ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡እንደዛ ያላት ልጅቷ በእድሜ በጣም ታላቁ ብትሆንም ገና እንዳያት በጣም ስለወደዳት ነበር…የዛን ጊዜ ስለእሷ የተሰማው ስሜት ዛሬም ድረስ በልቡ ላይ ተቋጥሮ እንደቆረቆረው ነው፡፡
ዞር ብላ አየችውና እጆቾን ዘርግታ ፀጉሩን እያሻሸች‹‹ጎረምሳው…ተከየፍክብኝ እንዴ?››ነበር ያለችው፡፡
እንደማፈር አለና …አቀርቅሮ ዝም አላት፡፡በወቅቱ ብዙ ነገር ሊመልስላት ፈልጎ ነበር፡፡ግን ከንፈሮቹ ተነቃንቀው ቃላት ከአንደበቱ ማውጣት አልቻሉም፡፡
‹‹አይዞኝ ስቀልድ ነው፡፡ለማንኛውም አሁን ሂዱና ተኙ፡፡.ነገ እናወራለን፡፡››
‹‹እሺ›› አሉና ሁላቱም ከግራና ከቀኞ ተነስተው ባዶ መሬት ላይ ዘና ብሎ በመዘረጋጋት ተኝቶ እያንኳራፋ ያለውን ቾንቤን በጎሪጥ እያዩ በስሩ አልፈው ወደመኝታቸው ሄዱ፡፡ኑሀሚና ናኦል ጥዋት ተነስተው አካባቢውን ሲቃኙ የለሊቷ ልጅ ተነስታ ልክ እንደደላው የቤት ልጅ ስፖርት እየሰራች ነበር ያገኞት፡፡…ሳንቾ በአካባቢው የለም፡፡ሌሎች ጓደኞቻቸው የተወሰኑት ተኝታዋል…የተቀሩትም ወደሚሄድበት ሄደዋል፡፡ለብሳው ያደሩትን አሮጌ ብርድልብስ እና ጆንያ ከስር የሚያነጥፉትን ካርቶን ስብስበውና አጣጥፈው ወደጥግ በማድረግ ዘወትር እንደሚያደርጉት በላዩ ላይ ድንጋይ ጭኑበት እና ወደልጅቷ ሄዱ ፡፡
‹‹እ ጩጬዎች ..ተነሳችሁ፡፡››በሚል ጥያቄ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡
‹‹አዎ…ቡሌ ፍለጋ ልንሄድ ነው… ትመጪያለሽ?››
‹‹አዎ…››አለችና እስፖርቷን አቋርጣ ..ፔስታሏን ያዘችና ተከተለቻቸው፡፡
‹‹እ የት ነው ምንበላው?
ሁለቱም አፍጥጠው አዮት‹‹እንዴ ገና ሆቴል ሄደን ተመላሽ ጠይቀን ነዋ››ኑሀሚ ነበረች በመኮሳተር የመለሰችላት፡፡
‹‹አይ ብር አለኝ ..ለምን ገዝተን አንበላም…፡፡››
ሁለቱም በደስታ ፈገግ አሉ…‹‹ስንት አለሽ..?››ናኦል ነበር ጠያቂው፡፡
‹‹ጅንስ ሱሪ ኪሷ ውስጥ እጇን ሰደደችና ሁለት መቶ ብር መዛ አወጣች…››
‹‹አይበቃም…››
‹‹አረ ይበቃል..ነይ ዝናሽ ጋር እንሂድ፡፡››
‹‹ዝናሽ ማነች…?››
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ሀሳቧን ሳትጨርስ ፊራኦል ከውጭ ስልኩን እየጎረጎረ መጥቶ ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ…ለረጅም ደቂቃዎች አላናገራትም …
‹‹ይሄን ያህል ምን ቢመስጥህ ነው?››
‹‹ባክሽ የድሮ መስሪያ ቤቴ..ማለቴ ቆርቆሮ ፋብሪካ ምናምን ብዬ አውርቼሽ ነበር አይደል?››
‹‹እ..ስለምትናፍቅህ ልጅ እያወራኸኝ ነው?››
‹‹አዎ ..ትክክክል?››
‹‹እና እሷ ምን ሆነች?››
‹‹እባክሽ ጠፋች…አንድ ብቸኛ ልጃቸው ጠፋችባቸው…ከዛሬ ነገ አገኛታለሁ ብዬ ስቃትት የእህቴንም ልብ ይዛ ጠፋች››
‹‹ጠፋች ማለት?››
‹‹እኔ እንጃ ..ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነው…ማህበራዊ ሚዲያው ሁሉ ስለእሷ ነው የሚያወራው››
‹‹ስለጠፋች ብቻ?››
‹‹አዎ አባትዬው ያለችበትን ለጠቆመ 5 ሚሊዬን ብር በሽልማት መልክ እክፍላለሁ ብሎ ስላሳወጀ ምድረ ዱርዬ ጠቅላላ መንገድ ላይ ያገኞትን ወጣት ሴት ሁሉ እያስቆሙ ከእሷ ፎቶ ጋር ማስተያያት ጀመረዋል፡፡››
‹‹እየቀለድክ መሆን አለበት?››
‹‹እውነቴን ነው…አታይውም እንዴ..?››ብሎ ስልኩን አቀበላት… ማህበራዊ ሚዲያውን የተቆጣጠረውን ሁለት ሶስት ፎቶዋን አየች…ውስጧን በረዳት…ግማሽ ፊቷ በፋሻ የተሸፈነ ቢሆንም አስተውሎ ያያት ሰው ሊለያት ይችላል…ፊቷ የተቀመጠው ፊራኦል እስከአሁን እንዴት እንዳለያት ተደንቃለች፡፡
ስልኩን መለሰችለት‹‹ምን ሆና ይሆን …..?የሀብታም ልጅ ነገር ይሄኔ ቀብጣ ሊሆን ይችላል?››ስትል አፏ ላይ እንደመጠላት ተናገረች፡፡
‹‹አይ እንደዛ እንኳን ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም…እሷ የሀብታም ልጅ ስለሆነች ነገሩ ጮኸ እንጂ በየቀኑ እኳ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች እዚህም እዛም ከያሉበት ተወስደው የሚጠለፉበት…በሰው ሚሊዬን ብር የሚጠየቅበት ሀገር ነው እኮ ያለነው….ስንቶች የተጠለፈባቸውን ልጃቸውን ወይም ባላቸውን ለማስመለስ ቤታቸውን ሸጠዋል…?ስንቶች የመኪናቸውን ሊቭሬ አስይዘው አራጣ ተበድረዋል….?.ንብረቱን አሟጦ ሸጦ ከከፈለስ በኋላ ስንቱ ሬሳ ተልኮለታለል…….እዚህ አገር በዚህ ጊዜ እየሆኑ ያሉትን ነገሮች እንኳን ለማውራት ለማሰብም ይከብዳ…እና ይህቺ ልጅ ምን እንደገጠማት ማንም የሚያውቅ የለም….፡፡››
‹‹እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን አላውቅም››
‹‹እንዴ!! ሀገር ውስጥ እየኖርሽ አልነበረም እንዴ…..?ክፍለሀገር ያለች የእናቱን ሞት ሰምቶ ሄዶ መቅበር ያልቻለ ስንት አለ….?ዘመድ ከዘመድ ከተቆራረጠ እኮ ቆየ፣ስንቱ የትውልድ አካባቢውን ሄዶ ለማየት ልክ እንደአውሮፓና አሜሪካ እንደመሄድ ከባድና የማይቻል ሆኖበታል…እና የዚህች ልጅ ቤተሰብ ጭንቀታቸውን ተመልከቺ…ስንቱን ያስባሉ… እህቴ ብትሆንስ ብዬ ሳስብ ዝግንን ይለኛል…እንደውም በቀደም የሰማሁትን ታሪክ ላጫውትሽ…››
በጉጉት ትኩረቷን ወደእሱ አቅንታ‹‹እሺ እየሰማሁህ ነው..››አለች ፡፡
ከአስር ወራት በፊት አዳማ አካባቢ ካለ አንድ የጠበል ቦታ ታጣቂዎቹ ድንገት ይመጡና የተወሰኑ ሰዎች አፍነው ይወስዳሉ፡፡ከተወሰዱት ውስጥ አንዱ ከአርሲ አካባቢ ነው የመጣው…የተጠየቀውን ብር ወላጆቹ በቀላሉ ማሟላት አይችሉም ቢሆንም ተለምኖና ከየሰው ተለቃቅሞ ከተጠየቀው ሩቡን ያህል ብር ለታጣቂዎች ይላክና የልጁ መለቀቅ ይጠበቃል..ግን ከዛሬ ነገ ይመጣል ሲባል ወራቶች ያልፋሉ፣..እናት እንቅልፍ ታጣለች…ቀንና ለሊት ማልቀስ ይሆናል ስራዋ…ልጇ ይኑር ይሙት የምትጠይቀው ሰውና የምታጣራበት መንገድ አልነበራትም…በመጨረሻ ሰው መፍትሔ ያለውን ይነግሯታል…የሞተ ሰው ነፍስ ጠርተው የሚያናግሩ ሰዎች ጋር ይዘዋት ይሄዳሉ…እንደተባለውም የልጇ ነፍስ ሲጠራ ይመጣል..‹‹አዎ እማዬ እኔ ልጅሽ ከሞትኩ 6 ወር አልፎኛል….እርምሽን አውጪ ይላታል››እናትም ወደቤቷ ተመልሳ ድንኳን ጥላ የልጇን እርም ታወጣለች…ዘመድ አዝማድ ሁሉ ለቅሶ ደርሶ እርማቸውን ያወጣሉ..በጣም የሚገርመው ምፀት ደግሞ ምን መሰለሽ እሷን ለቅሶ ለመድረስ ከሚመጡት የቅርብ ዘመዶቾ ውስጥ ሶስቱ ዳግመኛ በታጣቂዎች ተጠልፈው አረፉት፡፡››
ንግግሩ ይበልጥ ሆድ እንዲብሳት አደረጋት..እንባዋን ሊዘረገፍ ሲተናነቃት ተሰማት..
እሱ ንግግሩን ቀጠለ…‹‹አባዬ ይሄንን ባይሰማ ደስ ይለኛል…ከሰማ በጣም ነው የሚያዝነው….እሷን ሰፈራቸው ድረስ እየሄደ ከመኪና ስትወርድና ከቤት ስትወጣ እንደሚያያት አውቃለው…ልጄን በውስጧ ይዛለች..እሷን ሳያት ልጄ በከፊልም ቢሆን በህይወት እንዳለች ይሰማኝና እፅናናለው ይላል…ይገርምሻል እኔ እራሱ እንዲዚህ እንዳስብ ተፃዕኖ ያደረገብኝ እሱ ነው››
‹‹ይገርማል ….ግን ጋሼ ምን በሩቅ አሳያቸው ማለቴ እቤት ገብተው ቢያዮት እኮ ሰዎቹ የሚቃወሙ አይመስለኝም፡››
አዎ እንዳልሽው አይቃሙም ይሆናል..ግን አባዬ እኛን ፊት ለፊታቸው ካዩ ይሳቀቃሉ…ልጅቷ ፊት ከቀረብን ማልቀሳችን አይቀርም.. እሷ ፊት ማልቀስ ማለት ደግሞ ልጅቷ ልክ በሌላ ሰው ህይወት እንደምትኖር እንድታስብ ማድረግና ልጅቷን መጉዳት ነው….ሁላችንም ከእሷም ሆነ ከቤተሰቡ በስህተት እንኳን መገናኘት የለብንም ብሎ ቁርጥ ያለ ትዕዛዝ ለሁሉም አስተላልፏል…እኔንም ከዛ ፋብሪካ ስራዬን ጥዬ እንድወጣ ያስገደደኝ በዛ ምክንያት ነው፡፡አሁን አሁን ግን ያንን የእሱን ትዕዛዝ ለመጠበቅ እየተቸገርኩ ባለሁበት ሰዓት ነው…ይሄው አንደምታይው ልጅቷ የጠፋችው…››
‹‹‹በቃ ደከመኝ መሰለኝ ትንሽ ልተኛ ››ብላ አልጋ ልብሱን ወደላይ ሳበችና ሙሉ በሙሉ ተሸፈነችና ..በፀጥታ እንባዋን ዘረገፈች…አባትና እናቷ አሳዘኗት….ቢሆንም ለአመታ ያበሳጮትን ብስጭት ልትረሳላቸው አልቻለችም….በውሳኔዋ ፀንታ እስከመጨረሻው መቆየት እንዳለባት ዳግመኛ ወሰነች፡፡‹‹አዎ አሁን እያዩት ያሉት ስቃይ ይገባቸዋል››በማለት በረጅሙ ተነፈሰች፡፡
////
ሰለሞን በሶስተኛው ቀን አርፍዶ ሶስት ሰዓት አካባቢ ወደቢሮ እየሄደ ሳለ ስልኩ ጠራ…የማያውቀው አዲስ ቁጥር ነው…አነሳው፡፡
‹‹ኪያ የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ነው፡፡››ድርጅቱን ኪያ ብሎ የሰየመው አስቴርን ለማስደሰት ስለፈለገ ነበር…አስቴር እናቷ ከመሞታቸው በፊት ‹‹ኪያ ›› እያሉ ነበር የሚጠሯት እሱም አልፎ አልፎ ይሄንን ስም ይጠቀማል…ድርጅት ለመመስረት ሲያስብ ግን ወዲያው በምናብ የመጣለት ስም ይህ ኪያ የሚለው ስም ነው፡፡እንደምንም ብሎ አግብቶ ከእሷ ጋር አንድ ቤት መኖር ሲጀምሩ ደግሞ ሙሉ በሙሉ በወጥነት ኪያ የሚለውን ስም ይጠቃማል..ሚስቱም ሆነ ድርጅቱ በአንድ ስም ይጠራሉ…ይህ ነው እቅዱ፡፡
ሴሎቹ ሁሉ ተነቃቁ…‹‹በስተመጨረሻ ተሳካ…በስተመጨረሻ የመጀመሪያ ደንበኛዬን አገኘሁ….‹‹ሰሎሞን ጀግና ነህ፣›››ብሎ ተደሰተና ድምፁን ጎርነንና ሻከር አድርጎ፡፡‹‹አዎ ትክክል ኖት..ምን ልታዘዝ?፡፡››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እባኮት የቢሮዎትን ትክክለኛ አድርሻ ላስቸግሮት…?››
‹‹ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ 3ተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102 ፡››
‹‹አመሰግናለው ..ከ15 ደቂቃ በኃላ ደርሳለሁ›› ስልኩ ተዘጋ፡፡
እሱ ደግሞ ቢሮ ለመደርረስ 5 ደቂቃ ብቻ ነው የሚቀረው..
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ሀሳቧን ሳትጨርስ ፊራኦል ከውጭ ስልኩን እየጎረጎረ መጥቶ ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ…ለረጅም ደቂቃዎች አላናገራትም …
‹‹ይሄን ያህል ምን ቢመስጥህ ነው?››
‹‹ባክሽ የድሮ መስሪያ ቤቴ..ማለቴ ቆርቆሮ ፋብሪካ ምናምን ብዬ አውርቼሽ ነበር አይደል?››
‹‹እ..ስለምትናፍቅህ ልጅ እያወራኸኝ ነው?››
‹‹አዎ ..ትክክክል?››
‹‹እና እሷ ምን ሆነች?››
‹‹እባክሽ ጠፋች…አንድ ብቸኛ ልጃቸው ጠፋችባቸው…ከዛሬ ነገ አገኛታለሁ ብዬ ስቃትት የእህቴንም ልብ ይዛ ጠፋች››
‹‹ጠፋች ማለት?››
‹‹እኔ እንጃ ..ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነው…ማህበራዊ ሚዲያው ሁሉ ስለእሷ ነው የሚያወራው››
‹‹ስለጠፋች ብቻ?››
‹‹አዎ አባትዬው ያለችበትን ለጠቆመ 5 ሚሊዬን ብር በሽልማት መልክ እክፍላለሁ ብሎ ስላሳወጀ ምድረ ዱርዬ ጠቅላላ መንገድ ላይ ያገኞትን ወጣት ሴት ሁሉ እያስቆሙ ከእሷ ፎቶ ጋር ማስተያያት ጀመረዋል፡፡››
‹‹እየቀለድክ መሆን አለበት?››
‹‹እውነቴን ነው…አታይውም እንዴ..?››ብሎ ስልኩን አቀበላት… ማህበራዊ ሚዲያውን የተቆጣጠረውን ሁለት ሶስት ፎቶዋን አየች…ውስጧን በረዳት…ግማሽ ፊቷ በፋሻ የተሸፈነ ቢሆንም አስተውሎ ያያት ሰው ሊለያት ይችላል…ፊቷ የተቀመጠው ፊራኦል እስከአሁን እንዴት እንዳለያት ተደንቃለች፡፡
ስልኩን መለሰችለት‹‹ምን ሆና ይሆን …..?የሀብታም ልጅ ነገር ይሄኔ ቀብጣ ሊሆን ይችላል?››ስትል አፏ ላይ እንደመጠላት ተናገረች፡፡
‹‹አይ እንደዛ እንኳን ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም…እሷ የሀብታም ልጅ ስለሆነች ነገሩ ጮኸ እንጂ በየቀኑ እኳ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች እዚህም እዛም ከያሉበት ተወስደው የሚጠለፉበት…በሰው ሚሊዬን ብር የሚጠየቅበት ሀገር ነው እኮ ያለነው….ስንቶች የተጠለፈባቸውን ልጃቸውን ወይም ባላቸውን ለማስመለስ ቤታቸውን ሸጠዋል…?ስንቶች የመኪናቸውን ሊቭሬ አስይዘው አራጣ ተበድረዋል….?.ንብረቱን አሟጦ ሸጦ ከከፈለስ በኋላ ስንቱ ሬሳ ተልኮለታለል…….እዚህ አገር በዚህ ጊዜ እየሆኑ ያሉትን ነገሮች እንኳን ለማውራት ለማሰብም ይከብዳ…እና ይህቺ ልጅ ምን እንደገጠማት ማንም የሚያውቅ የለም….፡፡››
‹‹እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን አላውቅም››
‹‹እንዴ!! ሀገር ውስጥ እየኖርሽ አልነበረም እንዴ…..?ክፍለሀገር ያለች የእናቱን ሞት ሰምቶ ሄዶ መቅበር ያልቻለ ስንት አለ….?ዘመድ ከዘመድ ከተቆራረጠ እኮ ቆየ፣ስንቱ የትውልድ አካባቢውን ሄዶ ለማየት ልክ እንደአውሮፓና አሜሪካ እንደመሄድ ከባድና የማይቻል ሆኖበታል…እና የዚህች ልጅ ቤተሰብ ጭንቀታቸውን ተመልከቺ…ስንቱን ያስባሉ… እህቴ ብትሆንስ ብዬ ሳስብ ዝግንን ይለኛል…እንደውም በቀደም የሰማሁትን ታሪክ ላጫውትሽ…››
በጉጉት ትኩረቷን ወደእሱ አቅንታ‹‹እሺ እየሰማሁህ ነው..››አለች ፡፡
ከአስር ወራት በፊት አዳማ አካባቢ ካለ አንድ የጠበል ቦታ ታጣቂዎቹ ድንገት ይመጡና የተወሰኑ ሰዎች አፍነው ይወስዳሉ፡፡ከተወሰዱት ውስጥ አንዱ ከአርሲ አካባቢ ነው የመጣው…የተጠየቀውን ብር ወላጆቹ በቀላሉ ማሟላት አይችሉም ቢሆንም ተለምኖና ከየሰው ተለቃቅሞ ከተጠየቀው ሩቡን ያህል ብር ለታጣቂዎች ይላክና የልጁ መለቀቅ ይጠበቃል..ግን ከዛሬ ነገ ይመጣል ሲባል ወራቶች ያልፋሉ፣..እናት እንቅልፍ ታጣለች…ቀንና ለሊት ማልቀስ ይሆናል ስራዋ…ልጇ ይኑር ይሙት የምትጠይቀው ሰውና የምታጣራበት መንገድ አልነበራትም…በመጨረሻ ሰው መፍትሔ ያለውን ይነግሯታል…የሞተ ሰው ነፍስ ጠርተው የሚያናግሩ ሰዎች ጋር ይዘዋት ይሄዳሉ…እንደተባለውም የልጇ ነፍስ ሲጠራ ይመጣል..‹‹አዎ እማዬ እኔ ልጅሽ ከሞትኩ 6 ወር አልፎኛል….እርምሽን አውጪ ይላታል››እናትም ወደቤቷ ተመልሳ ድንኳን ጥላ የልጇን እርም ታወጣለች…ዘመድ አዝማድ ሁሉ ለቅሶ ደርሶ እርማቸውን ያወጣሉ..በጣም የሚገርመው ምፀት ደግሞ ምን መሰለሽ እሷን ለቅሶ ለመድረስ ከሚመጡት የቅርብ ዘመዶቾ ውስጥ ሶስቱ ዳግመኛ በታጣቂዎች ተጠልፈው አረፉት፡፡››
ንግግሩ ይበልጥ ሆድ እንዲብሳት አደረጋት..እንባዋን ሊዘረገፍ ሲተናነቃት ተሰማት..
እሱ ንግግሩን ቀጠለ…‹‹አባዬ ይሄንን ባይሰማ ደስ ይለኛል…ከሰማ በጣም ነው የሚያዝነው….እሷን ሰፈራቸው ድረስ እየሄደ ከመኪና ስትወርድና ከቤት ስትወጣ እንደሚያያት አውቃለው…ልጄን በውስጧ ይዛለች..እሷን ሳያት ልጄ በከፊልም ቢሆን በህይወት እንዳለች ይሰማኝና እፅናናለው ይላል…ይገርምሻል እኔ እራሱ እንዲዚህ እንዳስብ ተፃዕኖ ያደረገብኝ እሱ ነው››
‹‹ይገርማል ….ግን ጋሼ ምን በሩቅ አሳያቸው ማለቴ እቤት ገብተው ቢያዮት እኮ ሰዎቹ የሚቃወሙ አይመስለኝም፡››
አዎ እንዳልሽው አይቃሙም ይሆናል..ግን አባዬ እኛን ፊት ለፊታቸው ካዩ ይሳቀቃሉ…ልጅቷ ፊት ከቀረብን ማልቀሳችን አይቀርም.. እሷ ፊት ማልቀስ ማለት ደግሞ ልጅቷ ልክ በሌላ ሰው ህይወት እንደምትኖር እንድታስብ ማድረግና ልጅቷን መጉዳት ነው….ሁላችንም ከእሷም ሆነ ከቤተሰቡ በስህተት እንኳን መገናኘት የለብንም ብሎ ቁርጥ ያለ ትዕዛዝ ለሁሉም አስተላልፏል…እኔንም ከዛ ፋብሪካ ስራዬን ጥዬ እንድወጣ ያስገደደኝ በዛ ምክንያት ነው፡፡አሁን አሁን ግን ያንን የእሱን ትዕዛዝ ለመጠበቅ እየተቸገርኩ ባለሁበት ሰዓት ነው…ይሄው አንደምታይው ልጅቷ የጠፋችው…››
‹‹‹በቃ ደከመኝ መሰለኝ ትንሽ ልተኛ ››ብላ አልጋ ልብሱን ወደላይ ሳበችና ሙሉ በሙሉ ተሸፈነችና ..በፀጥታ እንባዋን ዘረገፈች…አባትና እናቷ አሳዘኗት….ቢሆንም ለአመታ ያበሳጮትን ብስጭት ልትረሳላቸው አልቻለችም….በውሳኔዋ ፀንታ እስከመጨረሻው መቆየት እንዳለባት ዳግመኛ ወሰነች፡፡‹‹አዎ አሁን እያዩት ያሉት ስቃይ ይገባቸዋል››በማለት በረጅሙ ተነፈሰች፡፡
////
ሰለሞን በሶስተኛው ቀን አርፍዶ ሶስት ሰዓት አካባቢ ወደቢሮ እየሄደ ሳለ ስልኩ ጠራ…የማያውቀው አዲስ ቁጥር ነው…አነሳው፡፡
‹‹ኪያ የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ነው፡፡››ድርጅቱን ኪያ ብሎ የሰየመው አስቴርን ለማስደሰት ስለፈለገ ነበር…አስቴር እናቷ ከመሞታቸው በፊት ‹‹ኪያ ›› እያሉ ነበር የሚጠሯት እሱም አልፎ አልፎ ይሄንን ስም ይጠቀማል…ድርጅት ለመመስረት ሲያስብ ግን ወዲያው በምናብ የመጣለት ስም ይህ ኪያ የሚለው ስም ነው፡፡እንደምንም ብሎ አግብቶ ከእሷ ጋር አንድ ቤት መኖር ሲጀምሩ ደግሞ ሙሉ በሙሉ በወጥነት ኪያ የሚለውን ስም ይጠቃማል..ሚስቱም ሆነ ድርጅቱ በአንድ ስም ይጠራሉ…ይህ ነው እቅዱ፡፡
ሴሎቹ ሁሉ ተነቃቁ…‹‹በስተመጨረሻ ተሳካ…በስተመጨረሻ የመጀመሪያ ደንበኛዬን አገኘሁ….‹‹ሰሎሞን ጀግና ነህ፣›››ብሎ ተደሰተና ድምፁን ጎርነንና ሻከር አድርጎ፡፡‹‹አዎ ትክክል ኖት..ምን ልታዘዝ?፡፡››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እባኮት የቢሮዎትን ትክክለኛ አድርሻ ላስቸግሮት…?››
‹‹ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ 3ተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102 ፡››
‹‹አመሰግናለው ..ከ15 ደቂቃ በኃላ ደርሳለሁ›› ስልኩ ተዘጋ፡፡
እሱ ደግሞ ቢሮ ለመደርረስ 5 ደቂቃ ብቻ ነው የሚቀረው..
#የጣት_ቁስል
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አንድ አይጠጣም
የወጣት ሰውነቱ ፣ ለግላጋ ቁመናው ፣ ተቀያይሯል፡፡ ከአሁን በፊት ያልነበረውን ፂም አውጥቷል፡፡ ታዲያ በጉንጮቹ ላይ ግራና ቀኝ የወረደው አሪዝ መሳይ ፂሙ ጳጳስ አስመስሎታል፡፡ እንኳን ለማያቀው ለሚያውቀውም ሰው ተመስገንን መለየት ያስቸግር ነበር፡፡
ምግብ አዝዘው እየበሉ ነው፡፡ መብላቱን ተወት አድርጎ በሆቴሉ ዲም ላይት ይገረማል፡፡
"ከተሜ ማለት እንደ ዚህ ነው እንዴ"? አለ ተመስን፡፡
የተለየ ነገር አየህ"? አለው ያሬድ፡፡
"እኛም አገር ነጫጭ ሰው አስተናጋጅ ሆኖ ሳይ ነው"፡፡
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ………...ትገርማለህ የአገርህን ሰው እንኳን መለየት አቃተህ፡፡ እነዚህ እኮ የእኛ አገር ሰዎች ናቸው፡፡ ቅባት ስለተቀባቡ ነው፡፡ ነጭ የመሰሉህ ብሎት ለምግብ ማወራረጃ ቢራ ለማዘዝ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ዞር አደረገ፡፡ ከአንድ መልከ መልካም ህንዳዊ ከምትመስል ቆንጆ ሴት ልጅ ጋር አይኖቹ ተጋጨ፡፡
"ማነሽ እህት ቢራ ታዘዥን" አላት፡፡
"እኔ እኮ ቢራ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ያሰክረኛል ፣ አልጠጣም፡፡ ለራስህ እዘዝ ፤ ለእኔ ጠጅ የለመድሁት ይሻለኛል፡፡ አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አይ! ተመስገን ትገርማለህ ፤ እኔ እኮ ብዙ የምታቅ ትመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ምንም አታውቅም፡፡ ጠጅ እኮ እንደዚህ ያለ ሆቴል ውስጥ አይሸጥም፡፡ አለማወቅህ ነው እንጅ ከጠጁ ቢራው ነው የሚሻለው፡፡ ባይሆን አንድ ጠጥተህ ትተወዋለህ፡፡ ብሎት ቢራ እንዲጠጣ አሳመነው፡፡
"ምን አይነት ቢራ ልታዘዛችሁ አለች፡፡ የተጠራችው መልከ መልካም የህንድ ቆንጆ የምትመስል አስተናጋጅ፡፡
"በእናንተ አገር መጀመሪያ ሰላምታ አይፈቀድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"ኧረ ! ይባላል፡፡ እሽ ይቅርታ ብላ የእጅ ሰላምታ ሰጠቻቸው፡፡ ለዛ ያለው ፈገግታዋ በታከለበት፡፡
"ስምሽ ማን ይባላል"? አላት ያሬድ፡፡ እጁን ከእጇ ሳያላቅቅ፡፡
"የሽሃረግ እባላለሁ" ፡፡
"እሽ አመሰግናለሁ ብሏት የራሱን ስም ሳይነግራት ሁለት ሐረር ቢራ አምጭልን አላት፡፡
የሽሃረግ አስተናጋጅ አይደለችም፡፡ አስተናጋጅዋ ወደ ሱቅ ወታለች፡፡ እስከ ምትመለስ ግን ወደ ሆቴሉ የሚገቡትን ተስተናጋጆች ታስተናግዳለች፡፡
ታዲያ የሆቴሉ አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይና ሐምራዊ የተቀላቀለ በሚመስለው ዲም ላይት ውስጥ ሽር ሽር እያለች ስታስተናግድ አትኩሮ ለተመለከታት ፤ የቀሚስ አለባበሷ ፤ ኢትዮጵያዊነቷን ያለቀቀ ሆኖ በሰው እጅ የተሰራ ሳይሆን ከለግላጋ ሰውነቷ ጋር አምላክ አብሮ የፈጠረው ይመስል ነበር፡፡
ተመስገን የሽሃረግ እጁን ከጨበጠችው በኋላ፤ ከባንኮኒው ስትወጣና ስትገባ አብሯት በአይኖቹ ይመላለሳል፡፡
"ሊያመኝ ነው መሰለኝ"? ፡፡
"ጠጣበት ይለቅሃል፡፡ ዘና በል ደግሞ እንደ ልጅ አገረድ አትሽኮርመም"፡፡ "ምነው ደግሞ አይንህን በልጅቷ ላይ የምታንጃብበው"? አለው ያሬድ፡፡
"ኧረ ! አላንጃበብኩም፡፡ ግን ጓደኛዋ የወንድ ሱሪ ነው ያጠለቀችው፡፡ እሷ ደግሞ እንዴው ሳያት አለባበሷ አገረኛውን አለቀቀም፡፡ ታምራለች" ፡፡
"የቤት ልጅ ሆና ይሆናል፡፡ አለ ፤ ያሬድ፡፡
ያሬድ የአልባሳት ንግድ ከጀመረ ብቻ ሳይሆን በፊትም ከእናት አባቱ ቤት እያለ ስለከተማ ሴቶች አንዳንድ ነገሮችን ያውቃል፡፡ ለከተማ አዲስ አይደለም፡፡
ተመስገን አንድ ቢራ ያሰክረኛል ብሎ እየፈራ ቢጠጣውም አንድ ቢራ ግን አላሰከረውም፡፡ ለመድገም ፈልጓል፡፡
"ለካ ቢራ እንደዚህ ይጣፍጣል እንዴ"? አለ፡፡ ከጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን እየጨለጠ፡፡
ቢራ እንግዴህ አንድ አይጠጣም፡፡ ከሰከርክም ከአሁን በኋላ ፤ ስለማንቀሳቀስ መቼም መኝታችን ድረስ ገብተን መተኛት አያቅተንም፡፡ ብሎት ቢራ ሊደግሙ የሽሃረግን ጠራት፡፡
የሽሃረግ ደግሞ አስተናጋጇን መቅደስን ጠርታ እዛጋ እየጠሩሽ ነው፡፡ ታዘዣቸው አለች፡፡
መቅደስ "ቢራ ይደገም"? አለች፡፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"እሷ ብዙም አታስተናግድም፡፡ ሂሳብ ነው የምትቀበለው፡፡ የማስተናግደው እኔ ነኝ ፡፡
"እሽ ሁለት ሐረር ድገሚን" ፡፡
ተመስገን የጥላሁን ገሰሰ "ያቺ ቆንጆ ጥርሰ በረዶናት ፤ ውብ አይናማ ናት፡፡ የሚለውን ቀዝቀዝ ያለ ዜማ ልቡን ወሰድ አድርጎታል፡፡ አይኖቹን በየሽሃረግ ላይ ማንከራተቱን አላቋረጠም፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"አሁን ከቅድሙ ድብርቱ ለቀቅ አላደረገህም ?
ካለቀቀህ ቢራውን ደጋግምበት፡፡ አልያም ሐገረኛ ሙዚቃ አስከፍተን እንጨፍራለን" አለ ፤ ያሬድ፡፡ የያዘውን ቢራ ጎንጨት እያደረገ፡፡ አንዳንድ ቢራ አልበቃቸውም፡፡ አራት አራቱን ቆነደዱት፡፡ ተመስገን ሞቅ እያለው መጣ፡፡
ያሬድ አገረኛ ሙዚቃ የለም እንዴ? አለ ፤ ለመቅደስ፡፡
"ልቀይርላችሁ"? ፡፡
"አዎ፤ በዚያውም ቢራ ይዘሽልን ነይ" ፡፡
አገረኛው ሙዚቃ ተከፈተ፡፡ ተነስተው ግን አልጨፈሩም፡፡ በተቀመጡበት አንገታቸውን ያወዛውዛሉ፡፡ የጠጣው ሐረር ቢራ መንፈሱን ሰረቅ አድርጎታል፡፡"ያች ኮረዳ ዝምብላ ታየኛለች" አለ ተመስገን፡፡ የራሱ አትኩሮ ማየት ሳይታወቀው፡፡
"የቷ ኮረዳ"? ፡፡
"ያቺ እዛ ውስጥ ተቀምጣ አንገቷን ብቻ የምትታየው፡፡ ስሟ ማን ነበር ያለችው"?
"የሽሃረግን ነው የምትለው"?፡፡
"አዎ፤ ትክክል ነህ፡፡ ቅድም እኮ ስትጠራት ሰምቼ አሁን አፌ ላይ ጠፍቶብኝ ነው፡፡
"የፈለግሃት ትመስላለህ፡፡ ለማንኛውም የሽሃረግን ለማግኘት መቅደስን መጥራት አለብን፡፡ በእጁ አጨብጭቦ መቅደስን ጠራት፡፡
"ልድገማችሁ" ብላ ጠየቀች መቅደስ፡፡ ቢራ ፈልገው መስሏት፡፡
"ቢራ እንኳን አልጨረስንም፡፡ ለየሽሃረግ አንድ ቢራ
ስጫት" አለ ፤ ያሬድ፡፡
ቢራ ጠጥታ አታውቅም፡፡ ለስላሳ ከሆነ ነው እንጅ ፡፡
"እሽ ፤ ስጫት" ፡:
መቅደስ የታዘዘችውን ለስላሳ ከፊሪጅ አውጥታ ሰጠቻት፡፡
ማነው ያዘዘሽ ; አለቻት የሽሃረግ?፡፡
"እዛጋ የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ናቸው የጋበዙሽ፡፡ ብላ እነ ያሬድን በእጇ አመለከተቻት፡፡ ደግሞ ስምሽን ያውቁታል፡፡ ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ እንዴ?
"ኧረ ! ካለ ዛሬ አላየኋቸውም፡፡ ቅድም ነው ሱቅ ሄደሽ ሳስተናግዳቸው ስምሽ ማነው ሲሉኝ የነገርኳቸው" አለች፡፡ በዲም ላይቱ ፈገግታ ተመስገንን በስርቆት እየተመለከተች፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በአብርሃም_ቃሉ
አንድ አይጠጣም
የወጣት ሰውነቱ ፣ ለግላጋ ቁመናው ፣ ተቀያይሯል፡፡ ከአሁን በፊት ያልነበረውን ፂም አውጥቷል፡፡ ታዲያ በጉንጮቹ ላይ ግራና ቀኝ የወረደው አሪዝ መሳይ ፂሙ ጳጳስ አስመስሎታል፡፡ እንኳን ለማያቀው ለሚያውቀውም ሰው ተመስገንን መለየት ያስቸግር ነበር፡፡
ምግብ አዝዘው እየበሉ ነው፡፡ መብላቱን ተወት አድርጎ በሆቴሉ ዲም ላይት ይገረማል፡፡
"ከተሜ ማለት እንደ ዚህ ነው እንዴ"? አለ ተመስን፡፡
የተለየ ነገር አየህ"? አለው ያሬድ፡፡
"እኛም አገር ነጫጭ ሰው አስተናጋጅ ሆኖ ሳይ ነው"፡፡
"ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ………...ትገርማለህ የአገርህን ሰው እንኳን መለየት አቃተህ፡፡ እነዚህ እኮ የእኛ አገር ሰዎች ናቸው፡፡ ቅባት ስለተቀባቡ ነው፡፡ ነጭ የመሰሉህ ብሎት ለምግብ ማወራረጃ ቢራ ለማዘዝ ከተቀመጠበት ወንበር ላይ አንገቱን ዞር አደረገ፡፡ ከአንድ መልከ መልካም ህንዳዊ ከምትመስል ቆንጆ ሴት ልጅ ጋር አይኖቹ ተጋጨ፡፡
"ማነሽ እህት ቢራ ታዘዥን" አላት፡፡
"እኔ እኮ ቢራ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ያሰክረኛል ፣ አልጠጣም፡፡ ለራስህ እዘዝ ፤ ለእኔ ጠጅ የለመድሁት ይሻለኛል፡፡ አለ ፤ ተመስገን፡፡
"አይ! ተመስገን ትገርማለህ ፤ እኔ እኮ ብዙ የምታቅ ትመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ምንም አታውቅም፡፡ ጠጅ እኮ እንደዚህ ያለ ሆቴል ውስጥ አይሸጥም፡፡ አለማወቅህ ነው እንጅ ከጠጁ ቢራው ነው የሚሻለው፡፡ ባይሆን አንድ ጠጥተህ ትተወዋለህ፡፡ ብሎት ቢራ እንዲጠጣ አሳመነው፡፡
"ምን አይነት ቢራ ልታዘዛችሁ አለች፡፡ የተጠራችው መልከ መልካም የህንድ ቆንጆ የምትመስል አስተናጋጅ፡፡
"በእናንተ አገር መጀመሪያ ሰላምታ አይፈቀድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"ኧረ ! ይባላል፡፡ እሽ ይቅርታ ብላ የእጅ ሰላምታ ሰጠቻቸው፡፡ ለዛ ያለው ፈገግታዋ በታከለበት፡፡
"ስምሽ ማን ይባላል"? አላት ያሬድ፡፡ እጁን ከእጇ ሳያላቅቅ፡፡
"የሽሃረግ እባላለሁ" ፡፡
"እሽ አመሰግናለሁ ብሏት የራሱን ስም ሳይነግራት ሁለት ሐረር ቢራ አምጭልን አላት፡፡
የሽሃረግ አስተናጋጅ አይደለችም፡፡ አስተናጋጅዋ ወደ ሱቅ ወታለች፡፡ እስከ ምትመለስ ግን ወደ ሆቴሉ የሚገቡትን ተስተናጋጆች ታስተናግዳለች፡፡
ታዲያ የሆቴሉ አረንጓዴ ፣ ቢጫ ፣ ቀይና ሐምራዊ የተቀላቀለ በሚመስለው ዲም ላይት ውስጥ ሽር ሽር እያለች ስታስተናግድ አትኩሮ ለተመለከታት ፤ የቀሚስ አለባበሷ ፤ ኢትዮጵያዊነቷን ያለቀቀ ሆኖ በሰው እጅ የተሰራ ሳይሆን ከለግላጋ ሰውነቷ ጋር አምላክ አብሮ የፈጠረው ይመስል ነበር፡፡
ተመስገን የሽሃረግ እጁን ከጨበጠችው በኋላ፤ ከባንኮኒው ስትወጣና ስትገባ አብሯት በአይኖቹ ይመላለሳል፡፡
"ሊያመኝ ነው መሰለኝ"? ፡፡
"ጠጣበት ይለቅሃል፡፡ ዘና በል ደግሞ እንደ ልጅ አገረድ አትሽኮርመም"፡፡ "ምነው ደግሞ አይንህን በልጅቷ ላይ የምታንጃብበው"? አለው ያሬድ፡፡
"ኧረ ! አላንጃበብኩም፡፡ ግን ጓደኛዋ የወንድ ሱሪ ነው ያጠለቀችው፡፡ እሷ ደግሞ እንዴው ሳያት አለባበሷ አገረኛውን አለቀቀም፡፡ ታምራለች" ፡፡
"የቤት ልጅ ሆና ይሆናል፡፡ አለ ፤ ያሬድ፡፡
ያሬድ የአልባሳት ንግድ ከጀመረ ብቻ ሳይሆን በፊትም ከእናት አባቱ ቤት እያለ ስለከተማ ሴቶች አንዳንድ ነገሮችን ያውቃል፡፡ ለከተማ አዲስ አይደለም፡፡
ተመስገን አንድ ቢራ ያሰክረኛል ብሎ እየፈራ ቢጠጣውም አንድ ቢራ ግን አላሰከረውም፡፡ ለመድገም ፈልጓል፡፡
"ለካ ቢራ እንደዚህ ይጣፍጣል እንዴ"? አለ፡፡ ከጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን እየጨለጠ፡፡
ቢራ እንግዴህ አንድ አይጠጣም፡፡ ከሰከርክም ከአሁን በኋላ ፤ ስለማንቀሳቀስ መቼም መኝታችን ድረስ ገብተን መተኛት አያቅተንም፡፡ ብሎት ቢራ ሊደግሙ የሽሃረግን ጠራት፡፡
የሽሃረግ ደግሞ አስተናጋጇን መቅደስን ጠርታ እዛጋ እየጠሩሽ ነው፡፡ ታዘዣቸው አለች፡፡
መቅደስ "ቢራ ይደገም"? አለች፡፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"እሷ ብዙም አታስተናግድም፡፡ ሂሳብ ነው የምትቀበለው፡፡ የማስተናግደው እኔ ነኝ ፡፡
"እሽ ሁለት ሐረር ድገሚን" ፡፡
ተመስገን የጥላሁን ገሰሰ "ያቺ ቆንጆ ጥርሰ በረዶናት ፤ ውብ አይናማ ናት፡፡ የሚለውን ቀዝቀዝ ያለ ዜማ ልቡን ወሰድ አድርጎታል፡፡ አይኖቹን በየሽሃረግ ላይ ማንከራተቱን አላቋረጠም፡
ድገሚን ሳይላት "የሽሃረግ አታስተናግድም እንዴ"? አላት ያሬድ፡፡
"አሁን ከቅድሙ ድብርቱ ለቀቅ አላደረገህም ?
ካለቀቀህ ቢራውን ደጋግምበት፡፡ አልያም ሐገረኛ ሙዚቃ አስከፍተን እንጨፍራለን" አለ ፤ ያሬድ፡፡ የያዘውን ቢራ ጎንጨት እያደረገ፡፡ አንዳንድ ቢራ አልበቃቸውም፡፡ አራት አራቱን ቆነደዱት፡፡ ተመስገን ሞቅ እያለው መጣ፡፡
ያሬድ አገረኛ ሙዚቃ የለም እንዴ? አለ ፤ ለመቅደስ፡፡
"ልቀይርላችሁ"? ፡፡
"አዎ፤ በዚያውም ቢራ ይዘሽልን ነይ" ፡፡
አገረኛው ሙዚቃ ተከፈተ፡፡ ተነስተው ግን አልጨፈሩም፡፡ በተቀመጡበት አንገታቸውን ያወዛውዛሉ፡፡ የጠጣው ሐረር ቢራ መንፈሱን ሰረቅ አድርጎታል፡፡"ያች ኮረዳ ዝምብላ ታየኛለች" አለ ተመስገን፡፡ የራሱ አትኩሮ ማየት ሳይታወቀው፡፡
"የቷ ኮረዳ"? ፡፡
"ያቺ እዛ ውስጥ ተቀምጣ አንገቷን ብቻ የምትታየው፡፡ ስሟ ማን ነበር ያለችው"?
"የሽሃረግን ነው የምትለው"?፡፡
"አዎ፤ ትክክል ነህ፡፡ ቅድም እኮ ስትጠራት ሰምቼ አሁን አፌ ላይ ጠፍቶብኝ ነው፡፡
"የፈለግሃት ትመስላለህ፡፡ ለማንኛውም የሽሃረግን ለማግኘት መቅደስን መጥራት አለብን፡፡ በእጁ አጨብጭቦ መቅደስን ጠራት፡፡
"ልድገማችሁ" ብላ ጠየቀች መቅደስ፡፡ ቢራ ፈልገው መስሏት፡፡
"ቢራ እንኳን አልጨረስንም፡፡ ለየሽሃረግ አንድ ቢራ
ስጫት" አለ ፤ ያሬድ፡፡
ቢራ ጠጥታ አታውቅም፡፡ ለስላሳ ከሆነ ነው እንጅ ፡፡
"እሽ ፤ ስጫት" ፡:
መቅደስ የታዘዘችውን ለስላሳ ከፊሪጅ አውጥታ ሰጠቻት፡፡
ማነው ያዘዘሽ ; አለቻት የሽሃረግ?፡፡
"እዛጋ የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ናቸው የጋበዙሽ፡፡ ብላ እነ ያሬድን በእጇ አመለከተቻት፡፡ ደግሞ ስምሽን ያውቁታል፡፡ ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ እንዴ?
"ኧረ ! ካለ ዛሬ አላየኋቸውም፡፡ ቅድም ነው ሱቅ ሄደሽ ሳስተናግዳቸው ስምሽ ማነው ሲሉኝ የነገርኳቸው" አለች፡፡ በዲም ላይቱ ፈገግታ ተመስገንን በስርቆት እየተመለከተች፡፡
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አላዛር በግንባታ ሰሎሜ ደግሞ በአካውንቲንግ በሌቭል 3 ከተመረቁ ወራቷች ተቆጠሩ፡፡ ሰሎሜ ስራ ለመቀጠር መባከን ብትጀምርም አላዛር ግን ለመቀጠር ሙከራ አላደረገም፡፡ቀጥታ ስራውን ነው አስፋፍቶ የቀጠለበት፡፡
ከምረቃው ከሶስት ወር በኃላ ሰፈራቸው በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደሚነሳ ተነገራቸው ፡፡በአንድ ወር ውስጥ ኮዬ ፈጬ ኮንደሚኒዬም ምትክ ቤት ተሰጣቸውና ወደእዛው እንዲዘዋወሩ ተደረገ፡፡ለሁለቱም ቤተሰቦች የተሰጣቸው ቤት አንድ ህንፃ ላይ ከመሆኑም በላይ አንድ ፍሎር ላይ ነው፡፡ሰሎሜና እናቷ ይሄ አጋጣሚ በመፈጠሩ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የተሰማቸው፡፡ የሚኖሩበት ቤት በየወሩ ኪራይ የሚከፈልበት የቀበሌ ቤት ቢሆንም ግን ደግሞ በተለይ ሰሎሜ እድሜ ልኳን የኖረችበት ሙሉ ትዝታዋ ያለበት.. የሳቀችበት.. ያለቀሰችበት የታመመችበት የዳነችበት የህይወቷን ጠቅላላ ታሪክ ተፅፎ የታተመበት ቤት በመሆኑ ስሜቷን ድፍርስርስ ነው ያደረገባት… ቢሆንም ግን አሁን በምትክ የተሰጣቸው ቤት የተሻለ ጥራት ያለው በመሆኑ እንደማካካሻ ቆጥራ በፀጋ ተቀበለችው፡፡
ለአላዛር ግን ልክ እንደሎተሪ ነው የቆጠረው፡፡ግድ ሆኖበት እንጂ ያንን ተወልዶ ያደገበትን ቤት አይወደውም..ከዛ ቤት ጋር በተያያዘ ካለው አስደሳች ትዝታ በእጥፍ ሀዘኑና ቁጭቱ ይበዛል፡፡በተለይ ቀጥታ አባቱን ስለሚያስታውሰው ሁሌ እንደቀፈፈውና የመቃብር ቤት አይነት ስሜት እንዲሰማው እንዳደረገው ነው፡፡እንደውም ከእዚህ ቤት ለመገላገል ሲል የራሱን የሆነ ቤት ለመግዛት የተለየ የባንክ ደብተር ከፍቶ ብር ማጠራቀም ከጀመረ አመት አልፏታል …፡፡ስለሆነም ዜናውን በደስታ ነው የተቀበለው፡፡ከዛ ቀጥታ ያደረገው የሱቅ ስራውን ላለማቋረጥ እዛው አካባቢ ሌላ ሱቅ በመከራየት እቃውን ወደእዛ ማዘዋወረና እቤቱን በደስታ አስረክቦ ወደኮዬ ፈጬ ጠቅልሎ ገባ፡፡በጣም አሪፉ አጋጣሚ ደግሞ በዛው ሰሞን በጣም የሚወዱት አያትዬው ህይወታቸው ስላለፉ ከበፊት ጀምሮ የልጅ ልጃቸውን ጥረቱና ትጋቱን ያዩ ስለነበረ ጠቀም ያለ የውርስ ገንዘብ ትተውለት ሞቱ ፡፡ከዛ ደረጃ 6 የኮንትራክተርነት ፍቃድ አወጣና የግንባታውን ዘርፍ ተቀላቀለ፡፡
///
ወደኮዬፌጬ ተዘዋውረው መኖር ከጀመሩ ከሁለት ወር በኃላ ነው፡፡
ስራ ውሎ ድክም ብሎት ወደ እቤት ገብቶ ሶፋው ላይ ጋደም እንዳለ በሩ ተቆረቆረ…በቅልጥፋና ሄዶ ከፈተው..እንደገመተው ሰሎሜ ነበረች፡፡
‹‹ግቢ›› አላትና በራፉን ክፍት ትቶላት ወደ ውስጥ ተመለሰና ሶፋው ላይ ተቀመጠ፡፡
በራፉን ዘጋችና ወደውስጥ ዘልቃ ዘላ ሶፋው ላይ በመውጣት ከጎኑ ተወሸቀች፡፡
ስሩ በመቀመጧ እና ሰውነቷ ከሰውነቱ በመነካካቱ በውስጡ እርካታ እየተሰማው በአንደበቱ ግን
‹‹ካልጠፋ ሶፋ ለምን ታጨናንቂኛለሽ?››አላት ፡፡
እንደማኩረፍ ብላ‹‹ጉረኛ ..አግኝተህ ነው?››አለችው ፡፡
‹‹አረ ባክሽ….?ለመሆኑ እንዲህ በተለየ ሁኔታ እየተፍለቀለቅሽ ያለሽው በምን ምክንያት ነው?››
‹‹ውይ በእቴቴ ሞት ያስታውቅብኛል እንዴ?››
‹‹በደንብ ነዋ…አንቺ እኮ ነሽ… ደስታሽም ሆነ ሀዘንሽ በግልፅ ነው ፊትሽ ላይ የሚፃፈው…ለመሆኑ ምን ተገኘ…?ብቻ ስራ አገኘሁ እንዳትይኝ?››
‹‹አንተ ደግሞ…እንዴት ብዬ ነው ስራ ማገኘው…ያው እዛው ካፌ እየሰራሁ ነው፡፡››
‹‹እና ምንድነው?››
‹‹ፍቅር ያዘኝ››
‹‹ምን?›› ብሎ በመደንገጥ ከጉልበቱ ላይ አሽቀንጥሮ አስነሳትና እግሮቹን ከሶፋው አውርዶ ቁጭ ብሎ አፈጠጠባት፡፡
አደነጋገጡ አስደነገጣት‹‹እንዴ ምን ያልኩህ መስሎህ ነው….?ፍቅር ያዘኝ እኮ ነው ያልኩህ››
‹‹ሰማሁሽ እኮ!!››
‹‹አይ አልሰማኸኝም.ኤሌክትሪክ ያዘኝ እንዳልኩህ እኮ ነው አደነጋገጥህ?››
‹‹እንዴ ምን ነካሽ? ኤሌክትሪክ ቢይዝሽ ይሻላል …አሁን ኤሌክትሪክ ቢይዝሽ ቆጣሪው አውቶማቲክ ስለሆነ ቶሎ ያጠፋል… ለጊዜው ተንዘርዝረሽ ወዲያው ታገግሚያለሽ…ፍቅር ግን ለዛውም በዚህ እድሜሽ!!››
‹‹በዚህ እድሜሽ….!ምን ለማለት ነው?››
‹‹ምን አስቸኮለሽ ለማለት ነዋ››
‹‹ሰውዬ..ስንት አመቴ ነው ታውቃለህ?››
‹‹እኔ እንጃ …ሀያ መሰለኝ››
‹‹አይደለም ሀያ ሶስት….ከእናንተ ጓደኛ ተብዬዎች ጋር ስንዘላዘል ተላልፎብኛል…››
‹‹እሺ ለመሆኑ አውቀዋለሁ….ማነው?››
‹‹ታውቀዋለህ….እስራኤል ነው››
‹‹እስራኤል …እስራኤል?››
‹‹ኮሌጅ እያለን አስተማሪያችን የነበረ፡፡››
‹‹እ እሱ ነው››አለ ቀዝቀዝ ብሎ ፡፡ተማሪ እያሉም አይኑን ይጥልባት እንደነበረ ታዝቧል…አሁን ኮሌጁን ሙሉ በሙሉ ለቀው ከተለዩ በኃላ በየት ዞረው እንደተገናኙ ምንም ሊገባው አልቻለም…፡፡
‹‹እና ምን ትላለህ?››
‹‹ምንም…በዚህ ዘመን አስተማሪ ማግባት ግን ጥሩ ነው?››አላት፡፡ይህን ያላት አስቦበት ሳይሆን ድንገት የሆነ ነገር ብሎ ጉዳዩን መቃወም ስላለበት ነው አፉ ላይ የመጣለትን የተናገረው፡፡
‹‹ምን ለማለት ነው ..?አስተማሪ ሰው አይደለም እንዴ…?.ደግሞ አፈቀርኩት አልኩህ እንጂ ላገባው ነው አልኩህ እንዴ?፡፡››
‹‹ያው ነው..ዛሬ ካፈቀርሺው ነገ ላግባው ማለትሽ ይቀራል?››
‹‹እና ብልስ ምን ችግር አለው?››
‹‹አይ ምንም ችግር የለውም..ከነጭ ድህነት ወደ ጥቁር ድህነት መሸጋገር ነው የሚሆንብሽ ብዬ ነው፡፡››
‹‹ብሽቅ የሆንክ ነገር ነህ፡፡ሰው ሁሉ አንደአንተ ብራም መሆን አለበት…?ፍቅር ደግሞ በገንዘብ አይገዛም››
‹‹ባክሽ እሱ ጊዜ ያለፈበት የድሮ አባባል ነው..በዚህ ዘመን ፍቅር ድብን አድርጎ በገንዘብ ይገዛል..እናም ደግሞ ድህነት የነበረን ፍቅር አባሮ ከልብ ያስወጣል፡››
‹‹እሱ ያንተ እምነት ነው..ለማንኛውም አፍቅሬዋለው.. ስላፈቀርኩትም በጣም ተደስቼለሁ..ደግሞ እኮ አንተም በእኔ መደሰት በጣም የምትደሰት መስሎኝ ነበር ዜናውን ላበስርህ እየበረርኩ የመጣሁት፡፡››አለችው በቅሬታ፡፡
..አፍቅሬዋለሁ እያለች ስታወራ ፊቷ ላይ ያለው ብርሀን ልዩ ነው፡፡‹‹ምን አለ እኔን አፍቅረሽ አብረን እንዲህ በደስታ ብናብረቀርቅ››ሲል በውስጡ አጉረመረመ፡፡እና እንደምንም እራሱን አረጋጋና ለእሷ ንግግር መልስ ይሰጥ ጀመረ‹‹ደስታሽ እንደሚያስደስተኝ አንቺም ታውቂያለሽ…ግን ደግሞ ለአንቺ የምመኝልሽ ዘላቂ ደስታ ነው…ዛሬ ለሳቅሽ ምክንያት የሆነ ነገር ነገ ሀዘን ላይ እንዲጥልሽ ለአልፈልግም….ለዛ ነው ሁሉን ነገር በጥንቀቃቄ እና በእርጋታ እንድትይዥው የምፈልገው፡፡››
እሷም ለስለስ አለችና ‹‹ለእኔ አስበህ እንደሆነ እኮ አውቃለው…ግን አታስብ እጠነቀቃለሁ…በል አሁን ቤት ስራ አለብኝ..እቴቴ ሳትጠራኝ ልሂድ››አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጩን ስማ ወደውጭ መራመድ ጀመረች…፡፡
አይኖቹ አብረዋት ተንከራተቱ….፡፡በሰማው መርዶ የዛለ ሰውነቱን እንደምንም ጎትቶ ከተቀመጠበት ተነሳና በራፉን ከውስጥ ቀርቅሮ ወደቦታው ተመለሰ፡፡30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በድንዛዜ አሰበ….ከዛ የሆነ ነገር አድርጎ ይሄንን ጉዳይ ማኮላሸት እንዳለበት ድምዳሜ ላይ ደረሰና .ስልኩን አነሳ፡፡ አንዳንድ ጉዳዬችን የሚያስፈፅምለት ልጅ ጋር ደወለ ስልኩ ተነሳ‹‹‹እንዴት ነህ…ከመሸ ደወልኩ ይቅርታ››
‹‹ሰላም ነኝ አላዛር ….ችግር የለውም….ምን ልታዘዝ?››
‹‹ለአንተ የሚሆን አንድ ስራ ነበረኝ፡፡››
‹‹ምንድነው?››
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================
አላዛር በግንባታ ሰሎሜ ደግሞ በአካውንቲንግ በሌቭል 3 ከተመረቁ ወራቷች ተቆጠሩ፡፡ ሰሎሜ ስራ ለመቀጠር መባከን ብትጀምርም አላዛር ግን ለመቀጠር ሙከራ አላደረገም፡፡ቀጥታ ስራውን ነው አስፋፍቶ የቀጠለበት፡፡
ከምረቃው ከሶስት ወር በኃላ ሰፈራቸው በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደሚነሳ ተነገራቸው ፡፡በአንድ ወር ውስጥ ኮዬ ፈጬ ኮንደሚኒዬም ምትክ ቤት ተሰጣቸውና ወደእዛው እንዲዘዋወሩ ተደረገ፡፡ለሁለቱም ቤተሰቦች የተሰጣቸው ቤት አንድ ህንፃ ላይ ከመሆኑም በላይ አንድ ፍሎር ላይ ነው፡፡ሰሎሜና እናቷ ይሄ አጋጣሚ በመፈጠሩ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የተሰማቸው፡፡ የሚኖሩበት ቤት በየወሩ ኪራይ የሚከፈልበት የቀበሌ ቤት ቢሆንም ግን ደግሞ በተለይ ሰሎሜ እድሜ ልኳን የኖረችበት ሙሉ ትዝታዋ ያለበት.. የሳቀችበት.. ያለቀሰችበት የታመመችበት የዳነችበት የህይወቷን ጠቅላላ ታሪክ ተፅፎ የታተመበት ቤት በመሆኑ ስሜቷን ድፍርስርስ ነው ያደረገባት… ቢሆንም ግን አሁን በምትክ የተሰጣቸው ቤት የተሻለ ጥራት ያለው በመሆኑ እንደማካካሻ ቆጥራ በፀጋ ተቀበለችው፡፡
ለአላዛር ግን ልክ እንደሎተሪ ነው የቆጠረው፡፡ግድ ሆኖበት እንጂ ያንን ተወልዶ ያደገበትን ቤት አይወደውም..ከዛ ቤት ጋር በተያያዘ ካለው አስደሳች ትዝታ በእጥፍ ሀዘኑና ቁጭቱ ይበዛል፡፡በተለይ ቀጥታ አባቱን ስለሚያስታውሰው ሁሌ እንደቀፈፈውና የመቃብር ቤት አይነት ስሜት እንዲሰማው እንዳደረገው ነው፡፡እንደውም ከእዚህ ቤት ለመገላገል ሲል የራሱን የሆነ ቤት ለመግዛት የተለየ የባንክ ደብተር ከፍቶ ብር ማጠራቀም ከጀመረ አመት አልፏታል …፡፡ስለሆነም ዜናውን በደስታ ነው የተቀበለው፡፡ከዛ ቀጥታ ያደረገው የሱቅ ስራውን ላለማቋረጥ እዛው አካባቢ ሌላ ሱቅ በመከራየት እቃውን ወደእዛ ማዘዋወረና እቤቱን በደስታ አስረክቦ ወደኮዬ ፈጬ ጠቅልሎ ገባ፡፡በጣም አሪፉ አጋጣሚ ደግሞ በዛው ሰሞን በጣም የሚወዱት አያትዬው ህይወታቸው ስላለፉ ከበፊት ጀምሮ የልጅ ልጃቸውን ጥረቱና ትጋቱን ያዩ ስለነበረ ጠቀም ያለ የውርስ ገንዘብ ትተውለት ሞቱ ፡፡ከዛ ደረጃ 6 የኮንትራክተርነት ፍቃድ አወጣና የግንባታውን ዘርፍ ተቀላቀለ፡፡
///
ወደኮዬፌጬ ተዘዋውረው መኖር ከጀመሩ ከሁለት ወር በኃላ ነው፡፡
ስራ ውሎ ድክም ብሎት ወደ እቤት ገብቶ ሶፋው ላይ ጋደም እንዳለ በሩ ተቆረቆረ…በቅልጥፋና ሄዶ ከፈተው..እንደገመተው ሰሎሜ ነበረች፡፡
‹‹ግቢ›› አላትና በራፉን ክፍት ትቶላት ወደ ውስጥ ተመለሰና ሶፋው ላይ ተቀመጠ፡፡
በራፉን ዘጋችና ወደውስጥ ዘልቃ ዘላ ሶፋው ላይ በመውጣት ከጎኑ ተወሸቀች፡፡
ስሩ በመቀመጧ እና ሰውነቷ ከሰውነቱ በመነካካቱ በውስጡ እርካታ እየተሰማው በአንደበቱ ግን
‹‹ካልጠፋ ሶፋ ለምን ታጨናንቂኛለሽ?››አላት ፡፡
እንደማኩረፍ ብላ‹‹ጉረኛ ..አግኝተህ ነው?››አለችው ፡፡
‹‹አረ ባክሽ….?ለመሆኑ እንዲህ በተለየ ሁኔታ እየተፍለቀለቅሽ ያለሽው በምን ምክንያት ነው?››
‹‹ውይ በእቴቴ ሞት ያስታውቅብኛል እንዴ?››
‹‹በደንብ ነዋ…አንቺ እኮ ነሽ… ደስታሽም ሆነ ሀዘንሽ በግልፅ ነው ፊትሽ ላይ የሚፃፈው…ለመሆኑ ምን ተገኘ…?ብቻ ስራ አገኘሁ እንዳትይኝ?››
‹‹አንተ ደግሞ…እንዴት ብዬ ነው ስራ ማገኘው…ያው እዛው ካፌ እየሰራሁ ነው፡፡››
‹‹እና ምንድነው?››
‹‹ፍቅር ያዘኝ››
‹‹ምን?›› ብሎ በመደንገጥ ከጉልበቱ ላይ አሽቀንጥሮ አስነሳትና እግሮቹን ከሶፋው አውርዶ ቁጭ ብሎ አፈጠጠባት፡፡
አደነጋገጡ አስደነገጣት‹‹እንዴ ምን ያልኩህ መስሎህ ነው….?ፍቅር ያዘኝ እኮ ነው ያልኩህ››
‹‹ሰማሁሽ እኮ!!››
‹‹አይ አልሰማኸኝም.ኤሌክትሪክ ያዘኝ እንዳልኩህ እኮ ነው አደነጋገጥህ?››
‹‹እንዴ ምን ነካሽ? ኤሌክትሪክ ቢይዝሽ ይሻላል …አሁን ኤሌክትሪክ ቢይዝሽ ቆጣሪው አውቶማቲክ ስለሆነ ቶሎ ያጠፋል… ለጊዜው ተንዘርዝረሽ ወዲያው ታገግሚያለሽ…ፍቅር ግን ለዛውም በዚህ እድሜሽ!!››
‹‹በዚህ እድሜሽ….!ምን ለማለት ነው?››
‹‹ምን አስቸኮለሽ ለማለት ነዋ››
‹‹ሰውዬ..ስንት አመቴ ነው ታውቃለህ?››
‹‹እኔ እንጃ …ሀያ መሰለኝ››
‹‹አይደለም ሀያ ሶስት….ከእናንተ ጓደኛ ተብዬዎች ጋር ስንዘላዘል ተላልፎብኛል…››
‹‹እሺ ለመሆኑ አውቀዋለሁ….ማነው?››
‹‹ታውቀዋለህ….እስራኤል ነው››
‹‹እስራኤል …እስራኤል?››
‹‹ኮሌጅ እያለን አስተማሪያችን የነበረ፡፡››
‹‹እ እሱ ነው››አለ ቀዝቀዝ ብሎ ፡፡ተማሪ እያሉም አይኑን ይጥልባት እንደነበረ ታዝቧል…አሁን ኮሌጁን ሙሉ በሙሉ ለቀው ከተለዩ በኃላ በየት ዞረው እንደተገናኙ ምንም ሊገባው አልቻለም…፡፡
‹‹እና ምን ትላለህ?››
‹‹ምንም…በዚህ ዘመን አስተማሪ ማግባት ግን ጥሩ ነው?››አላት፡፡ይህን ያላት አስቦበት ሳይሆን ድንገት የሆነ ነገር ብሎ ጉዳዩን መቃወም ስላለበት ነው አፉ ላይ የመጣለትን የተናገረው፡፡
‹‹ምን ለማለት ነው ..?አስተማሪ ሰው አይደለም እንዴ…?.ደግሞ አፈቀርኩት አልኩህ እንጂ ላገባው ነው አልኩህ እንዴ?፡፡››
‹‹ያው ነው..ዛሬ ካፈቀርሺው ነገ ላግባው ማለትሽ ይቀራል?››
‹‹እና ብልስ ምን ችግር አለው?››
‹‹አይ ምንም ችግር የለውም..ከነጭ ድህነት ወደ ጥቁር ድህነት መሸጋገር ነው የሚሆንብሽ ብዬ ነው፡፡››
‹‹ብሽቅ የሆንክ ነገር ነህ፡፡ሰው ሁሉ አንደአንተ ብራም መሆን አለበት…?ፍቅር ደግሞ በገንዘብ አይገዛም››
‹‹ባክሽ እሱ ጊዜ ያለፈበት የድሮ አባባል ነው..በዚህ ዘመን ፍቅር ድብን አድርጎ በገንዘብ ይገዛል..እናም ደግሞ ድህነት የነበረን ፍቅር አባሮ ከልብ ያስወጣል፡››
‹‹እሱ ያንተ እምነት ነው..ለማንኛውም አፍቅሬዋለው.. ስላፈቀርኩትም በጣም ተደስቼለሁ..ደግሞ እኮ አንተም በእኔ መደሰት በጣም የምትደሰት መስሎኝ ነበር ዜናውን ላበስርህ እየበረርኩ የመጣሁት፡፡››አለችው በቅሬታ፡፡
..አፍቅሬዋለሁ እያለች ስታወራ ፊቷ ላይ ያለው ብርሀን ልዩ ነው፡፡‹‹ምን አለ እኔን አፍቅረሽ አብረን እንዲህ በደስታ ብናብረቀርቅ››ሲል በውስጡ አጉረመረመ፡፡እና እንደምንም እራሱን አረጋጋና ለእሷ ንግግር መልስ ይሰጥ ጀመረ‹‹ደስታሽ እንደሚያስደስተኝ አንቺም ታውቂያለሽ…ግን ደግሞ ለአንቺ የምመኝልሽ ዘላቂ ደስታ ነው…ዛሬ ለሳቅሽ ምክንያት የሆነ ነገር ነገ ሀዘን ላይ እንዲጥልሽ ለአልፈልግም….ለዛ ነው ሁሉን ነገር በጥንቀቃቄ እና በእርጋታ እንድትይዥው የምፈልገው፡፡››
እሷም ለስለስ አለችና ‹‹ለእኔ አስበህ እንደሆነ እኮ አውቃለው…ግን አታስብ እጠነቀቃለሁ…በል አሁን ቤት ስራ አለብኝ..እቴቴ ሳትጠራኝ ልሂድ››አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጩን ስማ ወደውጭ መራመድ ጀመረች…፡፡
አይኖቹ አብረዋት ተንከራተቱ….፡፡በሰማው መርዶ የዛለ ሰውነቱን እንደምንም ጎትቶ ከተቀመጠበት ተነሳና በራፉን ከውስጥ ቀርቅሮ ወደቦታው ተመለሰ፡፡30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በድንዛዜ አሰበ….ከዛ የሆነ ነገር አድርጎ ይሄንን ጉዳይ ማኮላሸት እንዳለበት ድምዳሜ ላይ ደረሰና .ስልኩን አነሳ፡፡ አንዳንድ ጉዳዬችን የሚያስፈፅምለት ልጅ ጋር ደወለ ስልኩ ተነሳ‹‹‹እንዴት ነህ…ከመሸ ደወልኩ ይቅርታ››
‹‹ሰላም ነኝ አላዛር ….ችግር የለውም….ምን ልታዘዝ?››
‹‹ለአንተ የሚሆን አንድ ስራ ነበረኝ፡፡››
‹‹ምንድነው?››
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይ በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ ጠረን ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡
…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።
ዛሬ አዲስአለም እና ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡
አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡
ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡
መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/
አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/
ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል
ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››
የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››
ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው መጡበት፡፡
ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››
‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››
‹‹እሺ አናግረኝ…
‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››
‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››
‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››
‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡
‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››
‹‹ጓደኛሽ?››
‹‹ማ ፀዲ››
‹‹አዎ…››
‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››
‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››
‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››
‹‹ወደእናቷ ጋር፡››
‹‹በይ እንቺ ደውይላት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ፀደይ በንጋትገና ወፎች መንጫጫት ሲጀምሩ አንድም ኮሽታ ሳታሰማ በፀጥታ ከስሩ ሾልካ ወጣች፡፡ ሰውነቷ ደንጋይ ሲፈልጥ እንዳደረ ሰው ውልቅልቅ ብሏል።ክፍሉ በወሲብ ጠረን ታውዷል…ትናንት ማታ ወደ አንበሳው ጉድጓድ ውስጥ ሰተት ብላ ነበር በፍቃዷ የገባችው..እሱም ቆረጣጥሞ እና ቀረጣጥፎ በልቷታል፤ግን ደግሞ አድቅቋ አላጠፋትም….የማታው ታሪክ ወሲብ ብቻ ነበር - ደስ የሚል ጣፋጭ ወሲብ ። ሌሊቱን ሙሉ እንደዛ እራሷን ስታ እቅፉ ውስጥ ማሳለፍ አልነበረባትም። ለመራቅ የወሰነችው ይህ አይነት ቅርርብ ነበር።አንዳቸው ለሌላቸው ምንም ቃል አልገቡም፣ ። ስሟን እንኳን የማስታወስ እድሉ እስከ መቼ እንደሚቆይ እርግጠኛ አይደለችም? ‹ደግሞም አንድ ሰው ብዙ ልምምድ ካላደረገ በቀር እንዲህ ዓይነት ፍቅር መጠለፍ ውስጥ አይገባም› ስትል አሰበች።ከአልጋዋ ሾልካ ወጣች።ወለሉ መሀከል በባዶ እግሯ ምንጣፍ ላይ እርቃኗን ቆመች… .. አልጋው ላይ ተዘርሮ የሰላም እንቅልፍ የተኛውን ዘሚካኤልን አየችው፡፡ሰውነቷን ሙቀት ተሰማት፡፡አሁንም ቀስቅሳው ሰውነቷን ከሰውነቱ አጣብቃ ሌላ የሚያስጨነቅና የሚያቃት ወሲብ ብትሰራ ደስ ይላት ነበር…አዎ ቢያንስ አንድ የመጨረሻ የስሜት ጡዘትና ፍንዳታ የማስተናገድ እንጥፍጣፊ ጉልበትና ፍላጎት አታጣም፡፡ግን ራሷን ማቀብ አለባት.‹.በጣም ጣፋጭና የሚጥም ነገርን ከመጠን በላይ መጠቀም ለተውከት ይዳርጋል….፡፡›አለችና ቀጥታ ወደሻወር ሄደች ..ሙሉ እርቃን ሰውነቷን በሙሉ መስታወት ውስጥ ስታይ መደመም ውስጥ ገባች‹‹ፀዲ ግን የእውነት አንቺ ነሽ?››እራሷን በገረሜታ ጠየቀች….፡፡ትናንሽ ጡቷቾ ያለመደባቸውን ከመጠን በላይ ስለተጠቡና ስለታሹ ፍም መስለዋል፡፡ ከንፈሯም እንደዛው ሊፒስቲክ የተቀባች ይመስል ቀልተዋልም..በተወሰነ መጠንም የተንሻፈፈ እብጠት አብጠዋል፡፡ ሰውነቷ ላይ አልፎ አልፎ የተቧጨረ እና የቀላ ምልክት ይታያል.. ትናንት ወዲያ ለሰርጉ ዝግጅት ብላ ያን ሁሉ ብር ከስክሳ ለሳዕታት መከራ አይታ የተሰራችው ፀጉሯ አሁን እንዳይሆኑ ሆኖ እብዶች የጨፈሩበት የገለባ ክምር መስሏል፡፡
…እውነትም እንዳለው የሰውነቷ ቅርፃ በጣም ያምራል….እንደዚህ እርቃን ሰውነቷን ሙሉ መስታወት ፊት ቆማ አይታው አታውቅም…እና ብርቅ ሆኗባት ከፊትም ከኋላም እየተዟዟረች ተመለከተችው….በራሷ ተሰምቷት የማያውቀው በራስ የመታማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ከስሞና ተኖ ነበር ብላ የምታስበው ሴትነቷ ከተበታተነበት እየተሰባሰበ በመገጣጣም ላይ ያለች መሰላት፡፡ሽንቷን ሸናችና ፊቷን ተጣጥባ ..ተመልሳ ወደክፍሉ ተመለሰች..ቀሚሷን አንስታ ለበሰች፡፡ ፊት ለፊት ባገኘችው የደረሰኝ ብጫቂ ወረቀት ላይ ማስታወሻ ፅፋላት…ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች…፡፡በተቻለ መጠን በፍጥነት ከእሱ ለመራቅ ጓጓች።
ዛሬ አዲስአለም እና ሚካኤል የአዲስ አለም ቤተሰበች ጋር መልስ ተጠርተዋል..እና እዛ መልስ ላይ አብራቸው መሄድ ነበረባት…አሁን ባለችበት ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አትችልም፡፡ቀጥታ ወደቤቷ ሄዳ በራፏን ስትከፍት ገና ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ነበር፡፡ ቤቷን ከፍታ ገባችና ቀጥታ ወደ ሻወር ቤት ነው የገባችው ..ቀጥታ የለበሰችውን ቀሚስ አውልቃ ጥላ ሰውነቷን ታጠበችና ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ሄዳ የተለመደ አይነት አለባበሰዋን ጅንስ ሱሪ ከቲሸርት እና ከስኒከር ጫማ ጋር ለበሰችና የተወሰኑ ቅያሪ ልብሶችን በቦርሳዋ ከታ መልሳ ቤቱን ዘግታ ወጣች…፡፡ቀጥታ ወደ መነኸሪያ ነው የሄደችው፡፡አሁን ይሄን ከተማ ለቃ መሄድና እናቷን ጉያዋ ውስጥ ሆና የልጇን ጭንቅላት በማሻሸት በዚህ ሳምንት በተለይ ዛሬ ለሊት በህይወተዋ የገጠማትን ታአምራዊ ክስተት በስክነት ማሰብና ማጣጣም ትፈልጋለች፡፡ወደ ዶዶላ የሚወስዳት ባስ ውሰስጥ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ ስልኳን አወጣችና ለአዲስ አለም መልዕክት ለመላክ መፃፍ ጀመረች፡፡
አዲስ አዝናለው…ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ ወደእማዬ ጋር ሄጇለው…ከሶስት ቀን በኋላ ተመልሼ መጣለሁ….መልሱ ጋር አብሬችሁ ስላልሄድኩ ይቅርታ….ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆን ብኖርም ሙዳችሁን ነው የማበላሸው…
በጣም ወድሻለው…ሚኪን ይቅርታ ጠይቂልኝ፡፡
ፅፋ ጨረሰችና ላከችው…ወዲያው ስልኳን ጠረቀመችው…ማንም ደውሎ እንዲጨቀጭቃት አትፈልግም፡፡አሁን አዲስአለም ደውላ..‹‹ምን ሆነሽ ነው..?አዳርሽ እንዴት ነበር?››ብትላት ምን ብላ ትመልስላታለች…አይ አሁን እንደዛ አይነት መዳረቅ ውስጥ መግባት አቅሙ የላትም…ደስታና ትካዜ..እርካታና ቁዘማ ብቻ ፅንፍ የያዙ ድብልቅልቅ ስሜቷች ናቸው እየተሰማት ያለው፡፡፡ የተሳፈረችበት ባስ ልክ እሷ የነበረችበትን ስሜት የተረዳ ይመስል የሚኪያን ዘፍን ከፈተና በከፍተኛ ድምፅ በተነው፡፡
መስሎኝ ነበር ድሮ፤ ፍቅር ገራገር/2/
አፌን ፈታው ገና… ስላንተ ስናገር
ምን ቀረህ ልበልህ ፤ፀጉሬንም ቆጥረሀል/2/
ታሪኬን ገልብጠህ …እንደአዲስ ፈጥረሀል
ይሄ ዘፈን በዚህ ልክ ገብቷት አያውቅም ነበር…አብራ ማንጎራር ጀመረች…
///
ዘሚካኤል ከመኝታው ከተነሳና ጥላው እንደሄደች ካወቀ በኃላ ልብሱን ለባብሶ ቀጥታ መኪናውን እያሽከረከረ ወደወንድሙ ቤት ነው የሄደው፡፡
መኪና ውስጥ ሆኖ የመኪናውን ክላክስ ከመጠና በላይ ሲያንባርቅው የነአዲስአለም ሰራተኛ መጥታ የውጩና በራፍ ከፈተችና ..‹‹ምንድነው..ማንን ፈልገው ነው?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዲስአለምን ጥሪልኝ››
‹‹መኝታ ክፍል ውስጥ ነች ..አልተነሱም፡፡››
የትዕዛዝ ቃና ባለው ጠበቅ ያለ ቃል ‹‹አንኳኪና ቀስቅሻት››አላት፡፡
ልጅቷ እንደማቅማማት አለች‹‹ዘሚካኤል ይፈልግሻል በያት፡፡››
ዘሚካኤል የሚለውን ስም በመስማቷ በድንገት እንድትደነግጥ አደረጋት…ይሄ ስም ተደጋግሞ በቤቱ ውስጥ ሲጠራ ሰምታለች፡፡‹‹እሺ ይጠብቁኝ ››አለችና በራፉን ክፍት ጥላ ወደውስጥ ተመልሳ ሮጠች፡፡፡
ከደቂቃዎች በኃላ ሚካኤልና አዲስ አለም ከነቢጃማቸው ከኋላና ፊት ተከትለው መጡበት፡፡
ሚካኤል በራፉ ላይ ተገትሮ ሲቀር አዲስ አለም ወደዘሚካኤል ግዙፍ መኪና ተራመደች፡፡
ከድንጋጤና ግራ ከመጋባት ውስጥ ሳትወጣ‹‹ደህና አደርክ..?ምነው ..?ለምን ወደቤት አትገባም?፡፡››
‹‹አይ አልገባም..አንዴ ላናግርሽ ሰለፈለኩ ነው፡፡››
‹‹እሺ አናግረኝ…
‹‹መኪና ውስጥ ግቢያ››
‹‹ዞራ መኪና ውስጥ ስትገባ..ወንድሙን ዞር ብሎ ሳያየው መኪናውን አንቀሳቀሰና ወደፊት ነዳ‹‹እንዴ ምን እየሰራ ነው?››አዲስ አለም ጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››
‹‹ምንድነው የምፈራው ..አለባባሴን አታይም እንዴ …?በቢጃማ እኳ ነኝ››
‹‹ብዙም አንርቅም….መልሼ አመጣሻለው..››አለና አንድ ኪሎ ሜትር ከሰፈሯ ከራቀ በኃላ መኪናዋን ከአስፓልቱ አውጥቶ ዳር አቆመና ሞተሩን አጥፈ፡፡
‹‹ምን ሆነሀል ?ምን ተፈጠረ?››
‹‹ጓደኛሽ?››
‹‹ማ ፀዲ››
‹‹አዎ…››
‹‹ጥሩ …..እኔም ስለእሷ ልጠይቅህ እፈልግ ነበር..፡፡ምን አደረካት…?እሷ ለእኛ ጓደኛችን ብቻ ሳትሆን ለሁለታችንም እንደእህታችን ነች..እንዴት ታስቀይማታለህ?››
‹‹ምነው? አስቀየመኝ አለቺሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም የት አግኝቼያት..?ግን ድንገት ብን ብላ ከተማውን ለቃ ከሄደች የሆነ ነገር ሆናለች ማለት ነው››
‹‹ወደየት ነው ከተማውን ለቃ ሄደችው?፡፡››
‹‹ወደእናቷ ጋር፡››
‹‹በይ እንቺ ደውይላት››
‹‹ሞክሬ ነበር ስልኳ አይሰራም፡፡››
‹‹እና መሄዷን በምን አወቅሽ ››