#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
☝ትላንት በፅሁፍ ስህተት ክፍል 26 የተባመው ክፍል 16 ተብሎ ይነበብ።
..ዕለቱ ቅዳሜ ነው::መርካቶ የተለመደ የትርምስ የግርግርና የጫጫታ ሂደቷን ቀጥላለች። የገበያ ልውውጡ ተጧጡፏል። የበዓል ሰሞን ሩጫ
ጥድፊያ ግፊያ መዋከብ ነው፡፡ የቅቤ ተራም እንደዚሁ። ቅቤ በገረወይና እየወረደ እየተመዘነ አንዱ በሌላው ላይ ይመረጋል። የቅቤ ተራራ ገዥው በጣቱ ይቧጥጥና ወደ አፍንጫው እየወሰደ ለጋ ነው?ስማ ነው
?የቱ ይሻላል?" ይላል።
“እዚህ ይምጡ!ቆንጆ የወለጋ ቅቤ አለ!"
“ይኸው ለጋ የጎጃም! ለወጥ ከፈለጉ ደግሞ ዋጋው ይቀንሳል። ወደዚህ!'የ
ቅቤ ነጋዴዎች ከፊት ለፊታቸው በተከመረው የቅቤ ተራራ አናት ላይ እየ
ትንጠራሩ ይጣራሉ፡፡ በዚሁ መሀል ቅቤ ለመግዛት ሳይሆን የቅቤ ነጋዴ
የሚፈልግ ወጣት እዚህም እዚያም ይራወጥ ነበር፡፡ ጌትነት መኩሪያ. ..
“እባክህ የኔ ወንድም ከባሌ ጠቅላይ ግዛት ቅቤ የሚያመጡ ነጋዴ አቶ
ዓለሙ ተመስገን የሚባሉ ታውቃለህ?"
“አላውቃቸውም" ይሄንን ይተውና ደግሞ ሌሎቹን ይጠይቃል። "አናውቅም ይሉታል፡፡ ደግሞ ያስረዳል ልዩ ምልክታቸውን ቀይ ሽማግሌ መካከለኛ ቁመት ፀጉራቸው ትንሽ ወደ ውስጥ ገባ ያለ" ከዚህ ሁሉ መባዞንና ውትወታ በኋላ ባይቀናው ኖሮ አንጀቱ በተቃጠለ ነበር፡፡ በመጨረሻ ላይ አንድ የባሌ ሰው አገኘ፡፡
“እንዴ? ጋሼ አለሙ! ደንበኛዬ ናቸው ሰሞኑን ይመጣሉ ምነው በሰላም
ፈለካቸው?" የቅቤ ነጋዴው ከዲር ነበር፡፡
“ዘመዴ ናቸው በጣም ነው የምፈልጋቸው እንዴት አድርጌ ላገኛቸው እች
ላለሁ ባክህ?"
“ምን ችግር አለ ታዲያ ? እኔ አገናኝሃለሁ። ደንበኛዬ ናቸው እኔጋ ሳይደርሱ አይመለሱም። እስከዛሬ ድረስ መቆየታቸው ራሱ ገርሞኛል።
ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንደሚመጡ እርግጠኛ ነኝ"
“እንግዲያውስ እየተመላለስኩ እጠይቅሃለሁ። ለማንኛውም ጌትነት
መኩሪያ ብለህ ንገርልኝ" የከዲርን አድራሻ ተቀብሎ የራሱን አድራሻ ትቶ ተመለሰ፡፡ ጌትነት እንደዚያ በደስታ እየፈነደቀ ሽማግሌውን ፍለጋ የተሯሯጠው ያለምክንያት አልነበረም። የምስራቹን ሊያበስር ተጣድፎ ነበር፡፡ በሯን ጥርቅም አድርጋ ዘግታ ደጅ ስታስጠናው የከረመችው የስራ እድል የተረታችበት ያ ሁሉ ጭንቀት በሀሴት የተደመደመበት የሽመልስ ድካም በድል የተቋጨበት አስደሳች ቀን ነበር፡፡ ፈፅሞ ውድድር ሊባል በማያስችል ልዩነት ፈተናውን በማለፍ አድልዎ ወዳጆቿን ክፉኛ እንድ
ታጋልጣቸው ያደረገበት ልዩ ቀን... የዘመናት ወዳጃቸው ሀሰት ለነአቶ
አባይነህ ጀርባዋን የሰጠችበት ቀን! ጌትነት የተሰማው ደስታ ይህ ነው
አይባልም፡፡ በደስታው ላይ ደስታ የተሰማው ደግሞ ፀሀይ አስፋው ክፍት
ቦታ ሲገኝ በምትመጥንበት የስራ ደረጃ ላይ እንድትቀጠር የተሰጠውን
ተያያዥ ውሳኔ ሲሰማ ነበር። አንዱ ሲደሰት ሌላው መከፋቱ የማይቀር
ነው። ፀሀይ ፈተናውን አልፈሻል ተብላ ሥራውን ለመጀመር በተዘጋጀችበት
ወቅት በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት በጅዋ የገባው ሲሳይ ሲያመልጣት
ማዘኗ መሳቀቁ የማይቀር ነው። በሷ እግር ተተክቶ እሱ ኑሮውን ሲያሻሽል እሷ ደግሞ ልታዝን ልትከፋ በመሆኑ ደስታው ሙሉ ደስታ አይሆንለትም ነበር፡፡ ሽመልስ የፈተናውን ውጤትና የተወሰነውን ውሳኔ እንደ ሰማ ሳይውል ሳያድር ነበር ስልክ ደውሎ የጠራው፡፡
“እንኳን ደስ አለህ ጌትነት ዛሬ መንፈሴ እጅግ የረካበት ቀን ነው። ዛሬ ለኔ ትልቅ የድል ቀን ነው፡፡ ዐባይነህን ከመሰለ ዝሆን ጋር ታግዬ ልጥለው የቻልኩት በፈጣሪ ድጋፍና ባንተ ጥረት ነው። ሰራተኛው
በሙሉ ውጤቱን በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር የከረመው፡፡ ግማሹ አድናቆቱን
ሲገልፅ ግማሹ ደግሞ የአቶ አባይነህ ቲፎዞ በመሆን ጭፍን ጥላቻውን
ሲያንፀባርቅ ቆይቷል። እንደዚያ መሆኑ ግን በነገሩ እንድገፋበት ብርታት
ሆኖኝ እንጂ አላንበረከከኝም፡፡ አንተም አላሳፈርከኝም፡፡ ይሄ የጋራ ድካማችንና የጋራ ውጤታችን ነው፡፡ ከዚህ በሁዋላ
የዚህ ድርጅት አባል ነህ ትንሽ ነገር ልበልህ፡፡ በተቻለህ መጠን ከስራህ በስተቀር ሰዎች ለተንኮል
ለሌለብነት እንዲያመቻቸው ከሚፈጥሩት ቡድን ራስህን ጠብቅ። ስራህን
አክብር፡ ስራህ ያከብርሀል፡፡ በአለቃህ ፊት ብቻ ሰራተኛ መስለህ ለመታየት አትሞክር፡፡ አለቃህን በስርዓቱ ማክበር የሥራ ድርሻህን በብቃት መወጣት ተገቢ ነው፡፡ በማጎብደድ በእወደድ ባይነትና በወሬ አቀባባይነት ለመሾም ወይም ለማደግ የሚፈልጉ ሰዎች አርአያም ተከታይም ከመሆን ግን ራስህን ጠብቅ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ አለቃህ ስራህ መሆኑን ጠንቅቅህ መረዳት ይኖርብሃል፡፡ የአቶ አባይነህ ቲፎዞዎችና አንዳንድ ጭፍን አመለካከት ያላቸው ሰራተኞች ሊጠሉህና ሊተናኮሉህ ይችሉ ይሆናል።
መተናኮል ብቻም ሳይሆን ፊት ለፊት ሊበድሉህ ወይም ሊያጠቁህ ይሞክሩም ይሆናል ነገር ግን ጥቃትን በመፍራት ህሊናህ የማይፈቅደውን ነገር ከመስራት መቆጠብ ይኖርብሃል። አንተም አንድ ቀን በሃላፊነት ቦታ ላይ ስትቀመጥ ምን ማድረግ እንዳለብህ ከዚህ ትምህርት ልትወስድ ይገባል። ለማንኛውም መልካም የስራ ዘመን ይሁንልህ" በማለት የምስራቹን ካበሰረውና ተገቢውን ምክር ከለገሰው በኋላ አቅፎ ጀርባውን ቸብ
ቸብ አደረገው።
"በእውነት ነው የምልህ ሽመልስ አዲስ ህይወት የፈነጠቅክልኝ ስለኔ ሆነህ ራስህን ጎድተህ የተሟገትክልኝ ምንጊዜም የማከብርህ ወንድሜ
ነህ፡፡ ዓላማዬ የተሰጠኝን የሥራ ሀላፊነት በአግባቡ በመወጣት ትምህርቴን መቀጠልና የተሻለ ዕውቀት በመገብየት ራሴንም ቤተሰቤንም አገሬንም መርዳት ነው። ወደፊት ይህ ሁሉ ምኞቴ ተሳክቶ ለበለጠ ሀላፊነት በቅቼ ስዎችን ለመጥቀም ወይንም ለመጉዳት በሚያስችል የሥራ ሀላፊነት ላይ የመገኘት ዕድሉ የሚገጥመኝ ከሆነ ካንተ ከወንድሜ ያገኘሁት ትልቅ ትምህርት ምንጊዜም ከአእምሮዬ የሚጠፋ አይደለምና ስለ እውነት ለመሥራት ቃል እገባልሃለሁ" አለው።
ጌትነት የቅጥር ፎርማሊቲውን አሟልቶ ጨረስ፡፡ ስራ ይዞ ስው ለመሆን
ያደረገው ረጅም ሩጫ ዳር በመድረሱና ራሱን ችሎ ሌላውን የመርዳት ህልሙ እውን በመሆኑ ደስታው ወደር አልነበረውም፡፡ ልቡ ወደ ባሌ ወደ እናቱ ዘንድ በረረች፡፡ እህቱ ዘይኑን በቅርብ ክትትል የማስተማር ዕቅዱን በማሳካት ጉጉት ተውጦ ወደ ትውልድ መንደሩ በሀሳብ ከነፈ ያንን አስደሳች ዜና ለእናትና እህቱ ሊያሰማቸው ተጣድፎ አቶ አለሙን ለማግኘት በየቀኑና ቅቤና ነጋዴው ከዲር ዘንድ ሲመላለስ ከቆየ በኋላ ቀናው። በመጨረሻ ላይ አቶ አለሙ ዠ መምጣታቸውን አረጋገጠና በከዲር
አማካኝነት ተገናኙ።
“ጌትዬ! አንተ?! ደህና ነህ?! እንደው ነፍስህ አለ ልጄ?" የእናቱን ናፍቆት
ጭምር እቅፍ አድርገው አገላብጠው ሳሙት፡፡
"ደስ ብሎኛል አባባ ደስ ይበልዎ! የድሃዋ እናቴ አምላክ ጥሎ አልጣለኝም። ሥራ አገኘሁ! ሁሉንም ነገር ጨረስኩ! ሁሉንም ነገር ጨረስኩ!”
ሁለመናው ስቆ ደስታውን ገለፀላቸው፡፡ አቶ ዓለሙ በደስታ ዘለሉ፡፡
"ጎሽ! ጎሽ! እሰይ የኔ አንበሳ! እንኳን ደስ አለህ! እንዴት ያለውን የምስራች ነው የነገርከኝ ባክህ?! እሰይ! እስይ! እኔም ገዳም ሆንኩ ማለት ነው፡፡ የምስራች ሰምቼ የምስራች አብሳሪ ሆንኩ ማለት ነው። ጭንቅጰሲለኝ የከረመው የሷ ጉዳይ ነበር፡፡ መልካም ዜና አመጣልሻለሁ እንዳልኳት እንደፎከርኩት ተሳካልኝ ማለት ነው። ደስታው የሁላችንም ነው!” ፍንድቅድቅ አሉ።
"አባባ ለመሆኑ የጤናዋ ነገር እንዴት ነው? ሃሳቡ ገድሏታል መቼም
ጭንቅ ጥበብ እያለው ጠየቃቸው
“ደህና ነች ምንም አትልም ያንተ ነገር ነበር ሲያሳስባት የከረመው ከንግዲህ በኋላማ ምን ትጠይቀኛለህ?
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
☝ትላንት በፅሁፍ ስህተት ክፍል 26 የተባመው ክፍል 16 ተብሎ ይነበብ።
..ዕለቱ ቅዳሜ ነው::መርካቶ የተለመደ የትርምስ የግርግርና የጫጫታ ሂደቷን ቀጥላለች። የገበያ ልውውጡ ተጧጡፏል። የበዓል ሰሞን ሩጫ
ጥድፊያ ግፊያ መዋከብ ነው፡፡ የቅቤ ተራም እንደዚሁ። ቅቤ በገረወይና እየወረደ እየተመዘነ አንዱ በሌላው ላይ ይመረጋል። የቅቤ ተራራ ገዥው በጣቱ ይቧጥጥና ወደ አፍንጫው እየወሰደ ለጋ ነው?ስማ ነው
?የቱ ይሻላል?" ይላል።
“እዚህ ይምጡ!ቆንጆ የወለጋ ቅቤ አለ!"
“ይኸው ለጋ የጎጃም! ለወጥ ከፈለጉ ደግሞ ዋጋው ይቀንሳል። ወደዚህ!'የ
ቅቤ ነጋዴዎች ከፊት ለፊታቸው በተከመረው የቅቤ ተራራ አናት ላይ እየ
ትንጠራሩ ይጣራሉ፡፡ በዚሁ መሀል ቅቤ ለመግዛት ሳይሆን የቅቤ ነጋዴ
የሚፈልግ ወጣት እዚህም እዚያም ይራወጥ ነበር፡፡ ጌትነት መኩሪያ. ..
“እባክህ የኔ ወንድም ከባሌ ጠቅላይ ግዛት ቅቤ የሚያመጡ ነጋዴ አቶ
ዓለሙ ተመስገን የሚባሉ ታውቃለህ?"
“አላውቃቸውም" ይሄንን ይተውና ደግሞ ሌሎቹን ይጠይቃል። "አናውቅም ይሉታል፡፡ ደግሞ ያስረዳል ልዩ ምልክታቸውን ቀይ ሽማግሌ መካከለኛ ቁመት ፀጉራቸው ትንሽ ወደ ውስጥ ገባ ያለ" ከዚህ ሁሉ መባዞንና ውትወታ በኋላ ባይቀናው ኖሮ አንጀቱ በተቃጠለ ነበር፡፡ በመጨረሻ ላይ አንድ የባሌ ሰው አገኘ፡፡
“እንዴ? ጋሼ አለሙ! ደንበኛዬ ናቸው ሰሞኑን ይመጣሉ ምነው በሰላም
ፈለካቸው?" የቅቤ ነጋዴው ከዲር ነበር፡፡
“ዘመዴ ናቸው በጣም ነው የምፈልጋቸው እንዴት አድርጌ ላገኛቸው እች
ላለሁ ባክህ?"
“ምን ችግር አለ ታዲያ ? እኔ አገናኝሃለሁ። ደንበኛዬ ናቸው እኔጋ ሳይደርሱ አይመለሱም። እስከዛሬ ድረስ መቆየታቸው ራሱ ገርሞኛል።
ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንደሚመጡ እርግጠኛ ነኝ"
“እንግዲያውስ እየተመላለስኩ እጠይቅሃለሁ። ለማንኛውም ጌትነት
መኩሪያ ብለህ ንገርልኝ" የከዲርን አድራሻ ተቀብሎ የራሱን አድራሻ ትቶ ተመለሰ፡፡ ጌትነት እንደዚያ በደስታ እየፈነደቀ ሽማግሌውን ፍለጋ የተሯሯጠው ያለምክንያት አልነበረም። የምስራቹን ሊያበስር ተጣድፎ ነበር፡፡ በሯን ጥርቅም አድርጋ ዘግታ ደጅ ስታስጠናው የከረመችው የስራ እድል የተረታችበት ያ ሁሉ ጭንቀት በሀሴት የተደመደመበት የሽመልስ ድካም በድል የተቋጨበት አስደሳች ቀን ነበር፡፡ ፈፅሞ ውድድር ሊባል በማያስችል ልዩነት ፈተናውን በማለፍ አድልዎ ወዳጆቿን ክፉኛ እንድ
ታጋልጣቸው ያደረገበት ልዩ ቀን... የዘመናት ወዳጃቸው ሀሰት ለነአቶ
አባይነህ ጀርባዋን የሰጠችበት ቀን! ጌትነት የተሰማው ደስታ ይህ ነው
አይባልም፡፡ በደስታው ላይ ደስታ የተሰማው ደግሞ ፀሀይ አስፋው ክፍት
ቦታ ሲገኝ በምትመጥንበት የስራ ደረጃ ላይ እንድትቀጠር የተሰጠውን
ተያያዥ ውሳኔ ሲሰማ ነበር። አንዱ ሲደሰት ሌላው መከፋቱ የማይቀር
ነው። ፀሀይ ፈተናውን አልፈሻል ተብላ ሥራውን ለመጀመር በተዘጋጀችበት
ወቅት በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት በጅዋ የገባው ሲሳይ ሲያመልጣት
ማዘኗ መሳቀቁ የማይቀር ነው። በሷ እግር ተተክቶ እሱ ኑሮውን ሲያሻሽል እሷ ደግሞ ልታዝን ልትከፋ በመሆኑ ደስታው ሙሉ ደስታ አይሆንለትም ነበር፡፡ ሽመልስ የፈተናውን ውጤትና የተወሰነውን ውሳኔ እንደ ሰማ ሳይውል ሳያድር ነበር ስልክ ደውሎ የጠራው፡፡
“እንኳን ደስ አለህ ጌትነት ዛሬ መንፈሴ እጅግ የረካበት ቀን ነው። ዛሬ ለኔ ትልቅ የድል ቀን ነው፡፡ ዐባይነህን ከመሰለ ዝሆን ጋር ታግዬ ልጥለው የቻልኩት በፈጣሪ ድጋፍና ባንተ ጥረት ነው። ሰራተኛው
በሙሉ ውጤቱን በጉጉት ሲጠባበቅ ነበር የከረመው፡፡ ግማሹ አድናቆቱን
ሲገልፅ ግማሹ ደግሞ የአቶ አባይነህ ቲፎዞ በመሆን ጭፍን ጥላቻውን
ሲያንፀባርቅ ቆይቷል። እንደዚያ መሆኑ ግን በነገሩ እንድገፋበት ብርታት
ሆኖኝ እንጂ አላንበረከከኝም፡፡ አንተም አላሳፈርከኝም፡፡ ይሄ የጋራ ድካማችንና የጋራ ውጤታችን ነው፡፡ ከዚህ በሁዋላ
የዚህ ድርጅት አባል ነህ ትንሽ ነገር ልበልህ፡፡ በተቻለህ መጠን ከስራህ በስተቀር ሰዎች ለተንኮል
ለሌለብነት እንዲያመቻቸው ከሚፈጥሩት ቡድን ራስህን ጠብቅ። ስራህን
አክብር፡ ስራህ ያከብርሀል፡፡ በአለቃህ ፊት ብቻ ሰራተኛ መስለህ ለመታየት አትሞክር፡፡ አለቃህን በስርዓቱ ማክበር የሥራ ድርሻህን በብቃት መወጣት ተገቢ ነው፡፡ በማጎብደድ በእወደድ ባይነትና በወሬ አቀባባይነት ለመሾም ወይም ለማደግ የሚፈልጉ ሰዎች አርአያም ተከታይም ከመሆን ግን ራስህን ጠብቅ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ አለቃህ ስራህ መሆኑን ጠንቅቅህ መረዳት ይኖርብሃል፡፡ የአቶ አባይነህ ቲፎዞዎችና አንዳንድ ጭፍን አመለካከት ያላቸው ሰራተኞች ሊጠሉህና ሊተናኮሉህ ይችሉ ይሆናል።
መተናኮል ብቻም ሳይሆን ፊት ለፊት ሊበድሉህ ወይም ሊያጠቁህ ይሞክሩም ይሆናል ነገር ግን ጥቃትን በመፍራት ህሊናህ የማይፈቅደውን ነገር ከመስራት መቆጠብ ይኖርብሃል። አንተም አንድ ቀን በሃላፊነት ቦታ ላይ ስትቀመጥ ምን ማድረግ እንዳለብህ ከዚህ ትምህርት ልትወስድ ይገባል። ለማንኛውም መልካም የስራ ዘመን ይሁንልህ" በማለት የምስራቹን ካበሰረውና ተገቢውን ምክር ከለገሰው በኋላ አቅፎ ጀርባውን ቸብ
ቸብ አደረገው።
"በእውነት ነው የምልህ ሽመልስ አዲስ ህይወት የፈነጠቅክልኝ ስለኔ ሆነህ ራስህን ጎድተህ የተሟገትክልኝ ምንጊዜም የማከብርህ ወንድሜ
ነህ፡፡ ዓላማዬ የተሰጠኝን የሥራ ሀላፊነት በአግባቡ በመወጣት ትምህርቴን መቀጠልና የተሻለ ዕውቀት በመገብየት ራሴንም ቤተሰቤንም አገሬንም መርዳት ነው። ወደፊት ይህ ሁሉ ምኞቴ ተሳክቶ ለበለጠ ሀላፊነት በቅቼ ስዎችን ለመጥቀም ወይንም ለመጉዳት በሚያስችል የሥራ ሀላፊነት ላይ የመገኘት ዕድሉ የሚገጥመኝ ከሆነ ካንተ ከወንድሜ ያገኘሁት ትልቅ ትምህርት ምንጊዜም ከአእምሮዬ የሚጠፋ አይደለምና ስለ እውነት ለመሥራት ቃል እገባልሃለሁ" አለው።
ጌትነት የቅጥር ፎርማሊቲውን አሟልቶ ጨረስ፡፡ ስራ ይዞ ስው ለመሆን
ያደረገው ረጅም ሩጫ ዳር በመድረሱና ራሱን ችሎ ሌላውን የመርዳት ህልሙ እውን በመሆኑ ደስታው ወደር አልነበረውም፡፡ ልቡ ወደ ባሌ ወደ እናቱ ዘንድ በረረች፡፡ እህቱ ዘይኑን በቅርብ ክትትል የማስተማር ዕቅዱን በማሳካት ጉጉት ተውጦ ወደ ትውልድ መንደሩ በሀሳብ ከነፈ ያንን አስደሳች ዜና ለእናትና እህቱ ሊያሰማቸው ተጣድፎ አቶ አለሙን ለማግኘት በየቀኑና ቅቤና ነጋዴው ከዲር ዘንድ ሲመላለስ ከቆየ በኋላ ቀናው። በመጨረሻ ላይ አቶ አለሙ ዠ መምጣታቸውን አረጋገጠና በከዲር
አማካኝነት ተገናኙ።
“ጌትዬ! አንተ?! ደህና ነህ?! እንደው ነፍስህ አለ ልጄ?" የእናቱን ናፍቆት
ጭምር እቅፍ አድርገው አገላብጠው ሳሙት፡፡
"ደስ ብሎኛል አባባ ደስ ይበልዎ! የድሃዋ እናቴ አምላክ ጥሎ አልጣለኝም። ሥራ አገኘሁ! ሁሉንም ነገር ጨረስኩ! ሁሉንም ነገር ጨረስኩ!”
ሁለመናው ስቆ ደስታውን ገለፀላቸው፡፡ አቶ ዓለሙ በደስታ ዘለሉ፡፡
"ጎሽ! ጎሽ! እሰይ የኔ አንበሳ! እንኳን ደስ አለህ! እንዴት ያለውን የምስራች ነው የነገርከኝ ባክህ?! እሰይ! እስይ! እኔም ገዳም ሆንኩ ማለት ነው፡፡ የምስራች ሰምቼ የምስራች አብሳሪ ሆንኩ ማለት ነው። ጭንቅጰሲለኝ የከረመው የሷ ጉዳይ ነበር፡፡ መልካም ዜና አመጣልሻለሁ እንዳልኳት እንደፎከርኩት ተሳካልኝ ማለት ነው። ደስታው የሁላችንም ነው!” ፍንድቅድቅ አሉ።
"አባባ ለመሆኑ የጤናዋ ነገር እንዴት ነው? ሃሳቡ ገድሏታል መቼም
ጭንቅ ጥበብ እያለው ጠየቃቸው
“ደህና ነች ምንም አትልም ያንተ ነገር ነበር ሲያሳስባት የከረመው ከንግዲህ በኋላማ ምን ትጠይቀኛለህ?
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
... ታፈሡና መርዕድ መናኸሪያ ሲደርሱ ከምሽቱ አሥራ አንድ ሠዓት እየተጠጋ ነው:: ሁኔታው ግን የበለጠ ተባብሷል። እንዲያውም ሁለተኛው በራሪ
አውቶብስ ገብቶ ነገር ግን አሁንም ተላልፈው ኖራልና የተጠበቀው መረጃ ባለመገኘቱ ህገቡ ግራ ተጋብቶ ወለሌ ይላል። ይተረማመሳል፡፡ ይላቀሳል፡፡
ታፈሡ በሕዝቡ መሀል ክወዲያ ወዲህ እየተሯሯጠች «እህ እንዴት ነው? ምን ሰማችሁ! እንዴት ሰማችሁ ሰው ተርፎ ይሆን?» በማለት ስትርገበገብ ከኳኋኗን ይመለከት የነበረ አንድ ቀደም ብሎ ያውቃት የነበረ ሰው እጇን ያዝ አደረገና «ወይዘሮ ታፈሡ፣ አንቺም ሰው ሸኝተሽ ኖሯል? » ሲል ጠየቃት
«አዎ ጋሽ ዓለሙ! ወንድሜን፡፡» አለችው እጆቿን እያርገበገበች::
እግዜር ይጠብቅልሽ እንጂ የጉዳቱ መጠን እንኳ በጣም አሳሳቢ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ይኸው እስከ አሁን እንኳ የሰባት ሰው መርዶ ደረሰ፡፡»
ታፈሡ ወዲያው እጆቿን ወደ ላይ ዘርግታ «ወየው! ወየው ወየው
እያለች ልክ መርዶ የደረሳት ያህል ለይቶላት ታለቅስ ጀመር፡፡ እንባዋ በጉንጫ ላይ ቦይ ሰርቶ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ ጭንቅ ጥብብ፣ ብክን ክርትት ስትል የሚያያት ሁሉ
ልክ እንደ እሷው እንባውን ያዘራው ጀመር። በከተማው ውስጥ ታዋቂ እንደ መሆኗ ሴት ወንዱ ዙሪያዋን እየከበበ ሊያጽናናት ቢሞክርም እሷ ግን አንጀቷ እየተንሰፈሰፈ
አልረጋጋ ብላ አስቸገረች፡፡
ጀምበር ጠልቃ ለዓይን መያዝ ጀምረ፡፡ ቀሪው የዚያ ቦታ ትርዒች ስለ ነገው አስክሬን ፍለጋ ጉዞ መነጋገር ብቻ ሆነ። አንዱ ከሌላው ጋር ይመካከር ጀመር፡፡ ታፈሡና መርዕድም ሊሄዱ በጋራ ወሰኑ፡፡
ታፈሡና መርዕድ ወደ መናኸሪያ ከሄዱበት ሠዓት ጀምሮ ሄዋን ቢያንስ አሥር ጊዜ ከቤት እደጅ ወጣ ገባ ስትል ቆይታለች። ስጋት እያቁነጠነጣት ከተቀመጠችበት ይልቅ ስትቆም ስትራመድ ያሳለፈችው ጊዜ ይበልጣል:: መርዶ ይሆን ብሥራት የሚመጣላትን አታውቀውም፡፡ እነሱ ደግሞ ለእሷ ምንም ዓይነት
ፍንጭ ላለመስጠት እየተዘጋጁ ናቸው:: ሁለቱም ወደ ቤት እየተመለሱ በአሉባት ሰዓት ታፈሡ ያለቀስችበትን ዓይኗን ጭምቅ፣ ፊቷን ጥርግርግ አረገች። እንዲሁም ስለ ሁለት ሠዓት ዜና አስማም ተመካከሩ። በታፈሡ ቤት ሬዲዮ ላይከፈት፣ በዚያ ምትክ መርዕድ ቴፕ ሊከፍት፣ ታፈሡ ወደ ጎረቤት ሄዳ ዜና ሰምታ ልትመለስ።
የጠዋቱን ጉዞ በተመለከተ ታፈሡ ከባለቤቷ መልዕክት ተልኮላት ያን ልትቀበል ወደ አዲስ ኣበባ ልትሄድ መሆኗንና መርዕድ ጠዋት ይሸኛት ዘንድ እሷው ቤት ሊያድር ሆኖ የሔዋንን ጥርጣሬ ለመቀነስ ተዘጋጅተዋል፡፡
ከምሽቱ አንድ ሠዓት ላይ ታፈሡና መርዕድ ከቤት ሲደርሱ ሔዋን በር
ላይ ቆማ ስትጠብቃቸው አዩዋት፡፡ ታፈሡ የመጀመሪያውን ሔዋንን “ማረጋጊያ ዘዴ ወዲያው ፈጠረችና “ሔዩ! ቡና አላፈላች ይሆን? ብታይ የረባ ወሬ ላይገኝ ነገር ወዲያ ወዲህ ስንከራተት ስለ ቆየን ራሴን እንዴት ቀስፎ ይዞኛል መስለሽ አለቻት ወደ በር እየተራመደኝ፡፡ መርዕድ አጎንብሶ ከኋላዋ ይከተላል፡፡
«ምንም የለም?» አለች ሔዋን የበሩን መቃን ደገፍ ብላ እንደቆመች።
«ወሬማ ሞልቷል!ግን እርስ በእርሱ ይጋጫል»
«ምን ምን ይባላል ታፈሡዬ?»
«ጭራሽ የትኛው መኪና እንደተጋጨ እንኳ እልታወቀም»
ሦስቱም ወደ ቤት ገቡ፡፡ ሔዋንና መርዕድ ሶፋ ላይ ሲቀመጡ ታፈሡ ወደ ጓዳ ገባች ሠራተኛዋ የእራት ወጥ እየሰራች ነበርና ቶሎ በይና ቡና አፍይልኝ አለቻት ድምጿ ወደ ሳሎን እንዲሰማ አድርጋ ጮክ በማለት፡፡ ልብሷን ቀያይራ ወደ ሳሎን እየተመለሰች ሳለች መርዕድን «አዲስ እበባ የምትልከኝ ነገር ካለ አሁኑ ተዘጋጅ መርዕድ እያላችው ወደ ሶፋ ሄዳ ከሔዋን ጎን ተቀመጠች።
«መቼ ልትሄጂ?» አለቻት ሔዋን አዲስ ወሬ ሆኖባት በርገግ ብላ፡፡
ባለቤቴ ከርሞ ከርሞ ከውጭ ሀገር የሆነ ነገር ሳያልክ አይቀርም አዲስ አበባ መጥተሽ ወሰጂ ብለው ዛሬ በትምህርት ቤት በኩል ስልክ ደወሉልኝ»
«እና ነገ ልትሄጂ» አለች ሔዋን አሁንም ጭንቅ ጥብብ እያላት፡፡
«አዎ፣ ግን በጠዋት እንድትቀስቅሱኝ። መርዕድም እንዳሸኘኝ ብዬ እዚሁ ላሳድረው ነው ይዤው የመጣሁት። አለቻት ወደ መርዕድ አየት እያደረገች፡፡
«የኔስ ነገር ታፈሡዬ?»
«የአስቻለው ቁርጥ ሳይታወቅ ትሄጃለሽ እንዴ?» አለችና ታፈሡ እኔም እኮ ነገ ሄጂ ከነገ ወዲያ እመጣለሁ፡፡ እስከዚያው እዚሁ እኔ ቤት ሆነሽ ጠብቂኝ፡፡ አለቻት።
ሔዋን ነገሮች ሁሉ ተምታቱባት፡፡ ቀደም ሲል ያየችባቸው አስደንጋጭ ሁኔታና የአሁኑ እርጋታቸው ፈጽሞ ሊጣጣምላት አልቻለም። ጭራሽ የአስቻለውን
ነገር ማንሳት የነገር ደባል መፍጠር ሊመስልባት እንደሚችል እስከ መስጋት ደረሰች፡፡ ግን ደግሞ ሆድ ሆዷን በላትና «በዚያው ስለ አደጋውም ትሰሚያለሽ?» ስትል ታፈሡን ጠየቀቻት።
«የሆነ ነገር ካለማ ማየቴም አይቀርም፡፡ »አለችና ታፈሡ በተለይ ወደ መርዕድ አየት እያደረገች። «ግን እንደው ወሬው ሁሉ የማይጨበጥ ሆነና ግራ አጋባን እንጂ» አለች።
«ሰው ደሞ ዝም ብሎ ማዳነቅ ይወዳል፡፡» አለ መርዕድም ጣሪያ ጣሪያ እያየ የምንተ እፍረቱን ወዲያው ብድግ አለና ወደ ብፌው በመሄድ ሙዚቃ ከፈተ።
ከሌለህማን አለ እጀፈደጅህ ኪስህ ነው የቅርብ ወዳጅ» የሚለው ዜማ ሠሰማት ጀመረ።
እራት በልተው ሲጨርሱ ሁለት ሠዓት ሊሆን ተቃርቧል። የታፈሡ
"ሠራተኛ ቡና እያፈላች ሳለች ታፈሡ በጉጉት የምትጠብቀው የዜና ሠዓት ደረሰና መጣሁ ብላ ከቤት ውልቅ አለች፡፡ ከጎረቤቶቿ ቤት ስትደርስ ሬዲዮ ተከፍቶ የዜና
ንባብ ተጀምሯል። ታፈሡ በዚያ ቤት የተከበረች እንግዳ ናትና ከቤት ስትገባ ቤተሰቡ በሙሉ ተነስቶ ተቀበላት፡፡ ከሰላምታ በኋላ ሬዲዮው ሥር ቁጭ አለች።
ዜና ንባበ ቀጠለ። ዋና ዋና ዜናዎች ከአለቁ በኋላ «በመጨረሻም» እለ ዜና
አንባቢው ጋዜጠኛ
ዛሬ ከዲላ ወደ አዲስ እበባ ይጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከሞጆ ወደ ሻሸመኔ ይጓዝ ከነበረ መለስተኛ የህዝብ ሚመላለሻ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ በደረሰ አደጋ በትንሹ ሰላሳ ሶስት ሰዎች ሲሞቱ አርባ ስምንት ያህሉ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የዝዋይ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፁ:: ጽፈህት ቤቱ እንዳለው» ብሎ ሳይጨርስ ታፈሡ
ያንን ቤት በጨኸት አደበላለቀችው
እየዩ እኔ.. እየየ እኔ.. እየየ እኔ እያለች በወለሉ ላይ ድፍት አለች
ከዜናው ይልቅ በታፈሡ ሁኔታ የደነገጠው የዚያ ቤት ቤተሰብ በሙሉ ተረባርቦ ከተደፋችበት ቀና አድርጎ አስቀመጠ፡፡ «ምነው? ምነው?» አለ ሁሉም ሰው በማክታትል። ታፈሡ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ፋታ አላገኘችም፣ ስቅስቅ ብላ ታለቅስ ጀመር። አስቹ አርፈኸዋል! ተገላግለሃል ወንድሜ! የኔ ግልቱ የኔ ብስጨ! ወይኔ ! ወይኔ ! ወይኔ!» አለች በማከታተል::
«ምነው ወይዘሮ ታፈሡ ገና በግምት?» አሏት የቤቱ አባወራ ቀደ ብለው። «ምንሽ ነው ወይዘሮ ታፈሡ?» ሲሉ የቤቱ እማወራ ቀጠሉ፡፡ታፈሡ ግን ወደ ዝርዝር መግባት አልቻለችም፡፡ ተዉኝተዉኝ ተዉ በቃ ሌላ ሰው እይስማብኝ!» አለችና አደራ ጎረቤቶቼ ነገ እኔ እዚህ አልውልም ወደ ናዝሬት እሄዳለሁ:: ግን እዚህ እኔ ቤት ወስጥ ይኸን ጉድ መስማት የሌለባት ልጅ አለችና አደራ! የአሁኑን አኳኋኔን ለሠራተኛዬ እንኳ እንዳትነግሩብኝ አለቻቸውና እያለቀሰች ተስናብታቸው ወደ ቤቷ ተመለሰች::
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
... ታፈሡና መርዕድ መናኸሪያ ሲደርሱ ከምሽቱ አሥራ አንድ ሠዓት እየተጠጋ ነው:: ሁኔታው ግን የበለጠ ተባብሷል። እንዲያውም ሁለተኛው በራሪ
አውቶብስ ገብቶ ነገር ግን አሁንም ተላልፈው ኖራልና የተጠበቀው መረጃ ባለመገኘቱ ህገቡ ግራ ተጋብቶ ወለሌ ይላል። ይተረማመሳል፡፡ ይላቀሳል፡፡
ታፈሡ በሕዝቡ መሀል ክወዲያ ወዲህ እየተሯሯጠች «እህ እንዴት ነው? ምን ሰማችሁ! እንዴት ሰማችሁ ሰው ተርፎ ይሆን?» በማለት ስትርገበገብ ከኳኋኗን ይመለከት የነበረ አንድ ቀደም ብሎ ያውቃት የነበረ ሰው እጇን ያዝ አደረገና «ወይዘሮ ታፈሡ፣ አንቺም ሰው ሸኝተሽ ኖሯል? » ሲል ጠየቃት
«አዎ ጋሽ ዓለሙ! ወንድሜን፡፡» አለችው እጆቿን እያርገበገበች::
እግዜር ይጠብቅልሽ እንጂ የጉዳቱ መጠን እንኳ በጣም አሳሳቢ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ይኸው እስከ አሁን እንኳ የሰባት ሰው መርዶ ደረሰ፡፡»
ታፈሡ ወዲያው እጆቿን ወደ ላይ ዘርግታ «ወየው! ወየው ወየው
እያለች ልክ መርዶ የደረሳት ያህል ለይቶላት ታለቅስ ጀመር፡፡ እንባዋ በጉንጫ ላይ ቦይ ሰርቶ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ ጭንቅ ጥብብ፣ ብክን ክርትት ስትል የሚያያት ሁሉ
ልክ እንደ እሷው እንባውን ያዘራው ጀመር። በከተማው ውስጥ ታዋቂ እንደ መሆኗ ሴት ወንዱ ዙሪያዋን እየከበበ ሊያጽናናት ቢሞክርም እሷ ግን አንጀቷ እየተንሰፈሰፈ
አልረጋጋ ብላ አስቸገረች፡፡
ጀምበር ጠልቃ ለዓይን መያዝ ጀምረ፡፡ ቀሪው የዚያ ቦታ ትርዒች ስለ ነገው አስክሬን ፍለጋ ጉዞ መነጋገር ብቻ ሆነ። አንዱ ከሌላው ጋር ይመካከር ጀመር፡፡ ታፈሡና መርዕድም ሊሄዱ በጋራ ወሰኑ፡፡
ታፈሡና መርዕድ ወደ መናኸሪያ ከሄዱበት ሠዓት ጀምሮ ሄዋን ቢያንስ አሥር ጊዜ ከቤት እደጅ ወጣ ገባ ስትል ቆይታለች። ስጋት እያቁነጠነጣት ከተቀመጠችበት ይልቅ ስትቆም ስትራመድ ያሳለፈችው ጊዜ ይበልጣል:: መርዶ ይሆን ብሥራት የሚመጣላትን አታውቀውም፡፡ እነሱ ደግሞ ለእሷ ምንም ዓይነት
ፍንጭ ላለመስጠት እየተዘጋጁ ናቸው:: ሁለቱም ወደ ቤት እየተመለሱ በአሉባት ሰዓት ታፈሡ ያለቀስችበትን ዓይኗን ጭምቅ፣ ፊቷን ጥርግርግ አረገች። እንዲሁም ስለ ሁለት ሠዓት ዜና አስማም ተመካከሩ። በታፈሡ ቤት ሬዲዮ ላይከፈት፣ በዚያ ምትክ መርዕድ ቴፕ ሊከፍት፣ ታፈሡ ወደ ጎረቤት ሄዳ ዜና ሰምታ ልትመለስ።
የጠዋቱን ጉዞ በተመለከተ ታፈሡ ከባለቤቷ መልዕክት ተልኮላት ያን ልትቀበል ወደ አዲስ ኣበባ ልትሄድ መሆኗንና መርዕድ ጠዋት ይሸኛት ዘንድ እሷው ቤት ሊያድር ሆኖ የሔዋንን ጥርጣሬ ለመቀነስ ተዘጋጅተዋል፡፡
ከምሽቱ አንድ ሠዓት ላይ ታፈሡና መርዕድ ከቤት ሲደርሱ ሔዋን በር
ላይ ቆማ ስትጠብቃቸው አዩዋት፡፡ ታፈሡ የመጀመሪያውን ሔዋንን “ማረጋጊያ ዘዴ ወዲያው ፈጠረችና “ሔዩ! ቡና አላፈላች ይሆን? ብታይ የረባ ወሬ ላይገኝ ነገር ወዲያ ወዲህ ስንከራተት ስለ ቆየን ራሴን እንዴት ቀስፎ ይዞኛል መስለሽ አለቻት ወደ በር እየተራመደኝ፡፡ መርዕድ አጎንብሶ ከኋላዋ ይከተላል፡፡
«ምንም የለም?» አለች ሔዋን የበሩን መቃን ደገፍ ብላ እንደቆመች።
«ወሬማ ሞልቷል!ግን እርስ በእርሱ ይጋጫል»
«ምን ምን ይባላል ታፈሡዬ?»
«ጭራሽ የትኛው መኪና እንደተጋጨ እንኳ እልታወቀም»
ሦስቱም ወደ ቤት ገቡ፡፡ ሔዋንና መርዕድ ሶፋ ላይ ሲቀመጡ ታፈሡ ወደ ጓዳ ገባች ሠራተኛዋ የእራት ወጥ እየሰራች ነበርና ቶሎ በይና ቡና አፍይልኝ አለቻት ድምጿ ወደ ሳሎን እንዲሰማ አድርጋ ጮክ በማለት፡፡ ልብሷን ቀያይራ ወደ ሳሎን እየተመለሰች ሳለች መርዕድን «አዲስ እበባ የምትልከኝ ነገር ካለ አሁኑ ተዘጋጅ መርዕድ እያላችው ወደ ሶፋ ሄዳ ከሔዋን ጎን ተቀመጠች።
«መቼ ልትሄጂ?» አለቻት ሔዋን አዲስ ወሬ ሆኖባት በርገግ ብላ፡፡
ባለቤቴ ከርሞ ከርሞ ከውጭ ሀገር የሆነ ነገር ሳያልክ አይቀርም አዲስ አበባ መጥተሽ ወሰጂ ብለው ዛሬ በትምህርት ቤት በኩል ስልክ ደወሉልኝ»
«እና ነገ ልትሄጂ» አለች ሔዋን አሁንም ጭንቅ ጥብብ እያላት፡፡
«አዎ፣ ግን በጠዋት እንድትቀስቅሱኝ። መርዕድም እንዳሸኘኝ ብዬ እዚሁ ላሳድረው ነው ይዤው የመጣሁት። አለቻት ወደ መርዕድ አየት እያደረገች፡፡
«የኔስ ነገር ታፈሡዬ?»
«የአስቻለው ቁርጥ ሳይታወቅ ትሄጃለሽ እንዴ?» አለችና ታፈሡ እኔም እኮ ነገ ሄጂ ከነገ ወዲያ እመጣለሁ፡፡ እስከዚያው እዚሁ እኔ ቤት ሆነሽ ጠብቂኝ፡፡ አለቻት።
ሔዋን ነገሮች ሁሉ ተምታቱባት፡፡ ቀደም ሲል ያየችባቸው አስደንጋጭ ሁኔታና የአሁኑ እርጋታቸው ፈጽሞ ሊጣጣምላት አልቻለም። ጭራሽ የአስቻለውን
ነገር ማንሳት የነገር ደባል መፍጠር ሊመስልባት እንደሚችል እስከ መስጋት ደረሰች፡፡ ግን ደግሞ ሆድ ሆዷን በላትና «በዚያው ስለ አደጋውም ትሰሚያለሽ?» ስትል ታፈሡን ጠየቀቻት።
«የሆነ ነገር ካለማ ማየቴም አይቀርም፡፡ »አለችና ታፈሡ በተለይ ወደ መርዕድ አየት እያደረገች። «ግን እንደው ወሬው ሁሉ የማይጨበጥ ሆነና ግራ አጋባን እንጂ» አለች።
«ሰው ደሞ ዝም ብሎ ማዳነቅ ይወዳል፡፡» አለ መርዕድም ጣሪያ ጣሪያ እያየ የምንተ እፍረቱን ወዲያው ብድግ አለና ወደ ብፌው በመሄድ ሙዚቃ ከፈተ።
ከሌለህማን አለ እጀፈደጅህ ኪስህ ነው የቅርብ ወዳጅ» የሚለው ዜማ ሠሰማት ጀመረ።
እራት በልተው ሲጨርሱ ሁለት ሠዓት ሊሆን ተቃርቧል። የታፈሡ
"ሠራተኛ ቡና እያፈላች ሳለች ታፈሡ በጉጉት የምትጠብቀው የዜና ሠዓት ደረሰና መጣሁ ብላ ከቤት ውልቅ አለች፡፡ ከጎረቤቶቿ ቤት ስትደርስ ሬዲዮ ተከፍቶ የዜና
ንባብ ተጀምሯል። ታፈሡ በዚያ ቤት የተከበረች እንግዳ ናትና ከቤት ስትገባ ቤተሰቡ በሙሉ ተነስቶ ተቀበላት፡፡ ከሰላምታ በኋላ ሬዲዮው ሥር ቁጭ አለች።
ዜና ንባበ ቀጠለ። ዋና ዋና ዜናዎች ከአለቁ በኋላ «በመጨረሻም» እለ ዜና
አንባቢው ጋዜጠኛ
ዛሬ ከዲላ ወደ አዲስ እበባ ይጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከሞጆ ወደ ሻሸመኔ ይጓዝ ከነበረ መለስተኛ የህዝብ ሚመላለሻ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ በደረሰ አደጋ በትንሹ ሰላሳ ሶስት ሰዎች ሲሞቱ አርባ ስምንት ያህሉ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የዝዋይ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፁ:: ጽፈህት ቤቱ እንዳለው» ብሎ ሳይጨርስ ታፈሡ
ያንን ቤት በጨኸት አደበላለቀችው
እየዩ እኔ.. እየየ እኔ.. እየየ እኔ እያለች በወለሉ ላይ ድፍት አለች
ከዜናው ይልቅ በታፈሡ ሁኔታ የደነገጠው የዚያ ቤት ቤተሰብ በሙሉ ተረባርቦ ከተደፋችበት ቀና አድርጎ አስቀመጠ፡፡ «ምነው? ምነው?» አለ ሁሉም ሰው በማክታትል። ታፈሡ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ፋታ አላገኘችም፣ ስቅስቅ ብላ ታለቅስ ጀመር። አስቹ አርፈኸዋል! ተገላግለሃል ወንድሜ! የኔ ግልቱ የኔ ብስጨ! ወይኔ ! ወይኔ ! ወይኔ!» አለች በማከታተል::
«ምነው ወይዘሮ ታፈሡ ገና በግምት?» አሏት የቤቱ አባወራ ቀደ ብለው። «ምንሽ ነው ወይዘሮ ታፈሡ?» ሲሉ የቤቱ እማወራ ቀጠሉ፡፡ታፈሡ ግን ወደ ዝርዝር መግባት አልቻለችም፡፡ ተዉኝተዉኝ ተዉ በቃ ሌላ ሰው እይስማብኝ!» አለችና አደራ ጎረቤቶቼ ነገ እኔ እዚህ አልውልም ወደ ናዝሬት እሄዳለሁ:: ግን እዚህ እኔ ቤት ወስጥ ይኸን ጉድ መስማት የሌለባት ልጅ አለችና አደራ! የአሁኑን አኳኋኔን ለሠራተኛዬ እንኳ እንዳትነግሩብኝ አለቻቸውና እያለቀሰች ተስናብታቸው ወደ ቤቷ ተመለሰች::
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንም እንኳን ልጇ ደሕና መሆኑንና ትምህርትና ዋናም እየተማረ እንደሆነ፣ ከፍ ሲል ደግሞ ቀስት ውርወራ፣ ጉግስና አደን እንደሚማር ብትሰማም፣ ጭንቀቷ እምብዛም ሊቀንስላት አልቻለም። ሳታስበው ግን ሁኔታዎች ተቀየሩ። ለንጉሠ ነገሥቱ ቅርብ የሆነው ዐቃቤ ሰዐቱ ዲዮስቆሮስ ንጉሠ ነገሥቱን፣ “ኢያሱ መጥቶ የቤተመንግሥት ወግ፣
አስተዳደርና ትምርት በአግባቡ ይማር፤ ባባትዎ አጥንት ይዤዎታለሁ”እያለ አላስቆም አላስቀምጥ አላቸው።
ምንትዋብ አጋዥ ያገኘች መሰላት
አንድ ቀን ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ። የስድስት ዓመቱ ኢያሱ ሲጫወት ድንገት በቀስት የሰው ጊደር ወጋ። የጊደሩን ባለቤት ፈርቶ ከዐይን ተሰወረ። ሲፈለግ በመጥፋቱ ክርስትና አባቱ፣ የእህቱ ባል
ደጃዝማች ባስልዮስና የአካባቢው ነዋሪ በጭንቀት አካባቢውን አሰሱ::ሰፈርተኛው ሁሉ በደቦ ተከፋፍሎ ቀየውን፣ ወንዙንና ጫካውን ፈተሽ::ኢያሱ የውሃ ሽታ ሆነ። ሰዉ ተደናገጠ፣ የሚያደርገው ጠፋው። ብሎም
ኡኡታ፣ ለቅሶና ጩኸት በረከተ። ለንጉሠ ነገሥቱና ለምንትዋብ
እንዴት እንደሚነገራቸው ተመከረ።
ኢያሱ ከተደበቀበት ሲወጣ ዕልልታና ደስታ ጩኸትንና ለቅሶን
ተኩ። ማንነቱ ተደብቆ የኖረው ልጅ በዚህ አጋጣሚ ማንነቱ ታወቀ።
ደጃዝማች ባስልዮስ ግን የኢያሱ ማንነት መታወቁ አደገኛና አሳሳቢ
መሆኑን ተረድቶ በሐሳብ ማሰነ። አፄ በካፋ ጉዳዩን እንዲሰሙ አደረገ።ኢያሱም በፍጥነት ጐንደር እንዲመለስ ተደረገ። ምንትዋብ፣ እናቷና አያቷ የደስታና የእፎይታ እንባ አነቡ።
ምንትዋብ ሳትውል ሳታድር፣ ኢያሱ በተመረጡ አስተማሪዎች
ትምህርት እንዲማር አደረገች። የመንፈስ፣ የግብረገብ፣ የአካል ግንባታና የቤተመንግሥት ወግ ትምህርትም ላይ አተኮረች።
አፄ በካፋ ጠላቶቼ ይገድሉብኛል ብለው ስጋት ቢገባቸውም፣ ዝምታን ፈቀዱ። በሌላ በኩል ግን ከእሷ፣ ከእመቤት እንኰዬ፣ ከእመቤት ዮልያናና ከግራዝማች ኒቆላዎስ ጋር ብዙ ጊዜ ቆይታ መያዝ አዘወተሩ።
በተለይ ምንትዋብን፣ “አንቺ ብልህና አስተዋይ ስለ ሆንሽ እኔ ሳልኖር ኸልዤ ጋር ሁነሽ አገሬን ባግባቡ እንድትመሪ፣ እንድታስተዳድሪ።
የባሕር ማዶ አረመኔዎች አገሬ ገብተው እንዳይበጠብጡ፤ ሕዝቤንም በሃይማኖት ሆነ በሌላ እንዳይበክሉ ዐደራ” ይሏታል።
በነገሡ በዘጠነኛው ዓመት መጀመሪያ ላይ ጥቅምት ወር ውስጥ ግን፣
“ወዳጅ ዘመዴን እለያለሁ” በሚል ታመምኩ ብለው ሲደበቁ ምንትዋብ
ምሥጢር ጠበቀች። ወዲያው፣ “ንጉሡ ሊሞቱ ነው”፣ “ንጉሡ ሙተዋል” የሚል ወሬ ጐንደርን አወዛገባት። የጐንደር ከንቲባ ብላቴን ጌታ ኩቾ ከወህኒ አምባ ንጋሢ አመጣለሁ' ብሎ ሠራዊት አዘጋጀ። ወህኒ አምባዎች በበኩላቸው ወሬውን ሲሰሙ እኔ ልንገሥ፣ አንተ ንገሥ፣ የለም እሱ ይንገሥ ተባባሉ፤ ተመራረጡ፤ ተፎካከሩ።
ጐንደር እንደ ልማዷ ልትታመስ ሆነ።
በካፋ ይህን ሲሰሙ አለመታመማቸውን ለማሳየት ሐሙስ ቀን ደብረብርሃን ሥላሤ ሲሄዱ፣ መኳንንቱ በርቀት ከጋሻ ጃግሬዎች ኋላ በፈረስ ተከተሏቸው። ሕዝቡም ከየቤቱ እንደ ጎርፍ ፍንቅል ብሎ
ወጣ፡፡
በካፋ፣ ሕዝቡን፣ “ታዩኛላችሁና ወደየቤታችሁ ግቡ” ብለው አሰናበቱ።ሊቃውንት ንጉሠ ነገሥቱን በሕይወት በማየታቸው መሬት ሳሙ፤ካህናት ዘመሩ፤ ሕዝቡ ተደሰተ። ከረብሻ ዳነ። በካፋ ግን ብዙ ታዘቡ።
ወዳጅ መሳይ ሁሉ ከበስተጀርባቸው ምን እንደሚያስብ ተረዱ።
መኳንንቱን ወርቅ ሰቀላ ጠርተው፣ በአፈ ንጉሥ በኩል፣ “ምነው
ባካችሁ እንዳው ጥቂት ቀን ታምሜ ብተኛ ሽብር ማስነሳታችሁ? ስለምን ከተማዬን አስደነገጣችኋት? ሞተ ብላችሁ እንደዝኸ መሆናችሁ ተገቢ ነውን?” ሲሉ ጠየቋቸው። እንደማይተኙላቸውም ተረዱ። ሆኖም፣“እነዝኸ በልባቸው ክፋት የለም” ብለው ይቅርታ አደረጉላቸው።መሣሪያ ያነሳው ኩቾ ግን ከነተከታዮቹ ተይዞ ጊዜያዊ እስር ቤት ገብቶ ለፍርድ እንዲቀርብ ተወስኖበት ፍርድ ሸንጎ ቀረበ።
የሃገር ክህደት ወይም ሌላ ከፍተኛ ወንጀል ካልሆነ በስተቀር የዙፋን
ችሎት የማይዙት ንጉሠ ነገሥት፡ ጃን ተከል ተገኝተው ከምንትዋብ ጋር እንደወትሯቸው ቀይ ድባብ ተይዞላቸው፣ ከፍ ያለ ቦታ ላይ ተቀመጡ።መሣፍንቱ፣ መኳንንቱና ሊቃውንቱ እንደየደረጃቸው ተሰየሙ። ፍትሐ ነገሥት ተርጓሚዎቹ፣ ፍርድ ሰጭዎቹና አዛዦቹ፣ ግራ ቀኝ ተችዎቹ
ሁሉ ተገኝተዋል። ዐራቱ ሊቃውንት ፍትሐ ነገሥት ይዘው ቦታቸው
ላይ ተቀመጡ። አቡኑ፣ ዐቃቤ ሰዐቱና መኳንንቱ የተለመደ ቦታቸው ላይ ሆኑ።
ኩቾና ተከታዮቹ እግራቸው በእግረ ሙቅ ታስሮ፣ ጋሻ ጃግሬዎች
ግራና ቀኝ እየጠበቋቸው በንጉሠ ነገሥቱ ትይዩ ቆሙ።ከአዛዦቹ አንደኛው፣ “ጠበቃ ኸፈለግህ ይፈቀድልኻል” አለው፣
ኩቾን።
“አያሻኝም።”
“እንግዲያማ ተጠየቅ።”
“ልጠየቅ!”
“አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ። ኸዝኽ
እንዳትዛነፍ በቅሎ ያግድህ። ጃንሆይ ትንሽ አሟቸው ሰንብተው
እንደነበር አልሰማህም?”
“ሰምቻለሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ጃንሆይን አደባባይ ባታያቸው ሊሞቱ ነው ብለህ አላወራህም?”
“አላወራሁም።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ያለ ጃንሆይ ፈቃድ ሠራዊትህን ማንቀሳቀስ እንደማትችል
ታውቃለህ አታውቅም?”
“አውቃለሁ ።"
“ተጠየቅ!"
“ልጠየቅ!”
“ዛዲያ ስለምን ሠራዊትህን አንቀሳቅሰህ ለአመጥ ተነሳህ?”
“ለአመጥ አልተነሳሁም።”
“ምስክር ይጠራብህ?”
“ሠራዊት...”
"አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ ያልኩህን አጣርሰኻል። ለበቅሎ ዋስ ጥራ።”
“አላጣረስሁም።”
“አጣርሰኻል። ምስክር ይጠራብኝ ወይንም አይጠራብኝ ነበር
መልሱ።”
“ኸጥያቄህ አልወጣሁም። እማኞች ይጠሩልኝ” እያለ ወደ ሰዉ ተመለከተ ኩቾ።
“አጣርሷል! አጣርሷል! በቅሎዋን ይክፈል!” አለ፣ ሰዉ።
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ለአመጥ መሣሪያ አላነሳህም?”
“ራስ ተስፋ ኢየሱስና ቢትወደድ ስኩት ጃንሆይ ያስሩኻል ቢሉኝ
መሣሪያ አነሳሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ምንም ሳታደርግ ጃንሆይ ስለምን ያስሩኻል? ሞተዋል ብለህ
ስላስወራህና ኸወህኒ ነጋሢ ልታመጣ ስለፈለግህ ነው እነራስ ተስፋ ኢየሱስ ያስሩኻል ያሉህ።”
ኩቾ ወደ እፄ በካፋ ተመለከተ። ሁለት እጆቹን ዘርግቶ፣ “ጃንሆይ
ይማሩኝ” ብሎ አጎነበሰ።
“ምትጠይቀው ጥያቄ አለ?” ሲል ጠየቀው አንደኛው አዛዥ ።
“የለኝም። ምሕረት ያርጉልኝ ጃንሆይ!” አለ፣ ኩቾ፣ አጎንብሶ።
ከአዛዦቹ አንደኛው ጋቢውን አስተካከለና ወደ ንጉሠ ነገሥቱ
ተመለከተ፣ “ጃንሆይ ኩቾ የቀረበበት ክስ ክህደት ነው። ክህደት ደሞ በሞት ያስቀጣል” አለ፣ ፍትሐ ነገሥቱን እያገላበጠ። “ፍታ ነገሥቱ ሚለው በንጉሥ ላይ ያመጠና ያሳመጠ በሞት ይቀጣ ነው።”
ይህን ዓይነቱ የሞት ብይን ይገባዋል አይገባውም፤ ወይንም ደግሞ ሌላ ቅጣት ይቀጣ ብለው ለመወሰን መኳንንት እንደየማዕረጋቸው እየቆሙ ከዝቅተኛው ጀምሮ እስከ ከፍተኛው ድረስ አስተያየት ሰጡ።
“ክህደት ነውና ሞት ይገባዋል!” አሉ፣ አንደኛው መኰንን።
“ግዞት ይላክ!” አሉ፣ ሌላው።
“በግርፋት ይቀየርለት!” ብለው ተቀመጡ፣ አንደኛው
“ጃንሆይ መሐሪ ናቸውና ምህረት ይደረግለትና ሹመቱን ይገፈፍ”
አሉ፣ ሌላኛው።
እንደዚህ እያለ ሁሉም ተናግረው ከጨረሱ በኋላ፣ የማሳረጊያው
ንግግር የንጉሠ ነገሥቱ በመሆኑ፣ አፈ ንጉሡ አጎንብሶ ጆሮውን
ሲሰጣቸው ሁሉም ለመስማት ጆሯቸውን ሲያቀኑ ኩቾና ተከታዮቹ
ትንፋሻቸውን ውጠው ተጠባበቁ። ይህን ሁሉ በአንክሮ የምትመለከተው ምንትዋብም ተጠባበቀች።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንም እንኳን ልጇ ደሕና መሆኑንና ትምህርትና ዋናም እየተማረ እንደሆነ፣ ከፍ ሲል ደግሞ ቀስት ውርወራ፣ ጉግስና አደን እንደሚማር ብትሰማም፣ ጭንቀቷ እምብዛም ሊቀንስላት አልቻለም። ሳታስበው ግን ሁኔታዎች ተቀየሩ። ለንጉሠ ነገሥቱ ቅርብ የሆነው ዐቃቤ ሰዐቱ ዲዮስቆሮስ ንጉሠ ነገሥቱን፣ “ኢያሱ መጥቶ የቤተመንግሥት ወግ፣
አስተዳደርና ትምርት በአግባቡ ይማር፤ ባባትዎ አጥንት ይዤዎታለሁ”እያለ አላስቆም አላስቀምጥ አላቸው።
ምንትዋብ አጋዥ ያገኘች መሰላት
አንድ ቀን ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ። የስድስት ዓመቱ ኢያሱ ሲጫወት ድንገት በቀስት የሰው ጊደር ወጋ። የጊደሩን ባለቤት ፈርቶ ከዐይን ተሰወረ። ሲፈለግ በመጥፋቱ ክርስትና አባቱ፣ የእህቱ ባል
ደጃዝማች ባስልዮስና የአካባቢው ነዋሪ በጭንቀት አካባቢውን አሰሱ::ሰፈርተኛው ሁሉ በደቦ ተከፋፍሎ ቀየውን፣ ወንዙንና ጫካውን ፈተሽ::ኢያሱ የውሃ ሽታ ሆነ። ሰዉ ተደናገጠ፣ የሚያደርገው ጠፋው። ብሎም
ኡኡታ፣ ለቅሶና ጩኸት በረከተ። ለንጉሠ ነገሥቱና ለምንትዋብ
እንዴት እንደሚነገራቸው ተመከረ።
ኢያሱ ከተደበቀበት ሲወጣ ዕልልታና ደስታ ጩኸትንና ለቅሶን
ተኩ። ማንነቱ ተደብቆ የኖረው ልጅ በዚህ አጋጣሚ ማንነቱ ታወቀ።
ደጃዝማች ባስልዮስ ግን የኢያሱ ማንነት መታወቁ አደገኛና አሳሳቢ
መሆኑን ተረድቶ በሐሳብ ማሰነ። አፄ በካፋ ጉዳዩን እንዲሰሙ አደረገ።ኢያሱም በፍጥነት ጐንደር እንዲመለስ ተደረገ። ምንትዋብ፣ እናቷና አያቷ የደስታና የእፎይታ እንባ አነቡ።
ምንትዋብ ሳትውል ሳታድር፣ ኢያሱ በተመረጡ አስተማሪዎች
ትምህርት እንዲማር አደረገች። የመንፈስ፣ የግብረገብ፣ የአካል ግንባታና የቤተመንግሥት ወግ ትምህርትም ላይ አተኮረች።
አፄ በካፋ ጠላቶቼ ይገድሉብኛል ብለው ስጋት ቢገባቸውም፣ ዝምታን ፈቀዱ። በሌላ በኩል ግን ከእሷ፣ ከእመቤት እንኰዬ፣ ከእመቤት ዮልያናና ከግራዝማች ኒቆላዎስ ጋር ብዙ ጊዜ ቆይታ መያዝ አዘወተሩ።
በተለይ ምንትዋብን፣ “አንቺ ብልህና አስተዋይ ስለ ሆንሽ እኔ ሳልኖር ኸልዤ ጋር ሁነሽ አገሬን ባግባቡ እንድትመሪ፣ እንድታስተዳድሪ።
የባሕር ማዶ አረመኔዎች አገሬ ገብተው እንዳይበጠብጡ፤ ሕዝቤንም በሃይማኖት ሆነ በሌላ እንዳይበክሉ ዐደራ” ይሏታል።
በነገሡ በዘጠነኛው ዓመት መጀመሪያ ላይ ጥቅምት ወር ውስጥ ግን፣
“ወዳጅ ዘመዴን እለያለሁ” በሚል ታመምኩ ብለው ሲደበቁ ምንትዋብ
ምሥጢር ጠበቀች። ወዲያው፣ “ንጉሡ ሊሞቱ ነው”፣ “ንጉሡ ሙተዋል” የሚል ወሬ ጐንደርን አወዛገባት። የጐንደር ከንቲባ ብላቴን ጌታ ኩቾ ከወህኒ አምባ ንጋሢ አመጣለሁ' ብሎ ሠራዊት አዘጋጀ። ወህኒ አምባዎች በበኩላቸው ወሬውን ሲሰሙ እኔ ልንገሥ፣ አንተ ንገሥ፣ የለም እሱ ይንገሥ ተባባሉ፤ ተመራረጡ፤ ተፎካከሩ።
ጐንደር እንደ ልማዷ ልትታመስ ሆነ።
በካፋ ይህን ሲሰሙ አለመታመማቸውን ለማሳየት ሐሙስ ቀን ደብረብርሃን ሥላሤ ሲሄዱ፣ መኳንንቱ በርቀት ከጋሻ ጃግሬዎች ኋላ በፈረስ ተከተሏቸው። ሕዝቡም ከየቤቱ እንደ ጎርፍ ፍንቅል ብሎ
ወጣ፡፡
በካፋ፣ ሕዝቡን፣ “ታዩኛላችሁና ወደየቤታችሁ ግቡ” ብለው አሰናበቱ።ሊቃውንት ንጉሠ ነገሥቱን በሕይወት በማየታቸው መሬት ሳሙ፤ካህናት ዘመሩ፤ ሕዝቡ ተደሰተ። ከረብሻ ዳነ። በካፋ ግን ብዙ ታዘቡ።
ወዳጅ መሳይ ሁሉ ከበስተጀርባቸው ምን እንደሚያስብ ተረዱ።
መኳንንቱን ወርቅ ሰቀላ ጠርተው፣ በአፈ ንጉሥ በኩል፣ “ምነው
ባካችሁ እንዳው ጥቂት ቀን ታምሜ ብተኛ ሽብር ማስነሳታችሁ? ስለምን ከተማዬን አስደነገጣችኋት? ሞተ ብላችሁ እንደዝኸ መሆናችሁ ተገቢ ነውን?” ሲሉ ጠየቋቸው። እንደማይተኙላቸውም ተረዱ። ሆኖም፣“እነዝኸ በልባቸው ክፋት የለም” ብለው ይቅርታ አደረጉላቸው።መሣሪያ ያነሳው ኩቾ ግን ከነተከታዮቹ ተይዞ ጊዜያዊ እስር ቤት ገብቶ ለፍርድ እንዲቀርብ ተወስኖበት ፍርድ ሸንጎ ቀረበ።
የሃገር ክህደት ወይም ሌላ ከፍተኛ ወንጀል ካልሆነ በስተቀር የዙፋን
ችሎት የማይዙት ንጉሠ ነገሥት፡ ጃን ተከል ተገኝተው ከምንትዋብ ጋር እንደወትሯቸው ቀይ ድባብ ተይዞላቸው፣ ከፍ ያለ ቦታ ላይ ተቀመጡ።መሣፍንቱ፣ መኳንንቱና ሊቃውንቱ እንደየደረጃቸው ተሰየሙ። ፍትሐ ነገሥት ተርጓሚዎቹ፣ ፍርድ ሰጭዎቹና አዛዦቹ፣ ግራ ቀኝ ተችዎቹ
ሁሉ ተገኝተዋል። ዐራቱ ሊቃውንት ፍትሐ ነገሥት ይዘው ቦታቸው
ላይ ተቀመጡ። አቡኑ፣ ዐቃቤ ሰዐቱና መኳንንቱ የተለመደ ቦታቸው ላይ ሆኑ።
ኩቾና ተከታዮቹ እግራቸው በእግረ ሙቅ ታስሮ፣ ጋሻ ጃግሬዎች
ግራና ቀኝ እየጠበቋቸው በንጉሠ ነገሥቱ ትይዩ ቆሙ።ከአዛዦቹ አንደኛው፣ “ጠበቃ ኸፈለግህ ይፈቀድልኻል” አለው፣
ኩቾን።
“አያሻኝም።”
“እንግዲያማ ተጠየቅ።”
“ልጠየቅ!”
“አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ። ኸዝኽ
እንዳትዛነፍ በቅሎ ያግድህ። ጃንሆይ ትንሽ አሟቸው ሰንብተው
እንደነበር አልሰማህም?”
“ሰምቻለሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ጃንሆይን አደባባይ ባታያቸው ሊሞቱ ነው ብለህ አላወራህም?”
“አላወራሁም።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ያለ ጃንሆይ ፈቃድ ሠራዊትህን ማንቀሳቀስ እንደማትችል
ታውቃለህ አታውቅም?”
“አውቃለሁ ።"
“ተጠየቅ!"
“ልጠየቅ!”
“ዛዲያ ስለምን ሠራዊትህን አንቀሳቅሰህ ለአመጥ ተነሳህ?”
“ለአመጥ አልተነሳሁም።”
“ምስክር ይጠራብህ?”
“ሠራዊት...”
"አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ ያልኩህን አጣርሰኻል። ለበቅሎ ዋስ ጥራ።”
“አላጣረስሁም።”
“አጣርሰኻል። ምስክር ይጠራብኝ ወይንም አይጠራብኝ ነበር
መልሱ።”
“ኸጥያቄህ አልወጣሁም። እማኞች ይጠሩልኝ” እያለ ወደ ሰዉ ተመለከተ ኩቾ።
“አጣርሷል! አጣርሷል! በቅሎዋን ይክፈል!” አለ፣ ሰዉ።
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ለአመጥ መሣሪያ አላነሳህም?”
“ራስ ተስፋ ኢየሱስና ቢትወደድ ስኩት ጃንሆይ ያስሩኻል ቢሉኝ
መሣሪያ አነሳሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ምንም ሳታደርግ ጃንሆይ ስለምን ያስሩኻል? ሞተዋል ብለህ
ስላስወራህና ኸወህኒ ነጋሢ ልታመጣ ስለፈለግህ ነው እነራስ ተስፋ ኢየሱስ ያስሩኻል ያሉህ።”
ኩቾ ወደ እፄ በካፋ ተመለከተ። ሁለት እጆቹን ዘርግቶ፣ “ጃንሆይ
ይማሩኝ” ብሎ አጎነበሰ።
“ምትጠይቀው ጥያቄ አለ?” ሲል ጠየቀው አንደኛው አዛዥ ።
“የለኝም። ምሕረት ያርጉልኝ ጃንሆይ!” አለ፣ ኩቾ፣ አጎንብሶ።
ከአዛዦቹ አንደኛው ጋቢውን አስተካከለና ወደ ንጉሠ ነገሥቱ
ተመለከተ፣ “ጃንሆይ ኩቾ የቀረበበት ክስ ክህደት ነው። ክህደት ደሞ በሞት ያስቀጣል” አለ፣ ፍትሐ ነገሥቱን እያገላበጠ። “ፍታ ነገሥቱ ሚለው በንጉሥ ላይ ያመጠና ያሳመጠ በሞት ይቀጣ ነው።”
ይህን ዓይነቱ የሞት ብይን ይገባዋል አይገባውም፤ ወይንም ደግሞ ሌላ ቅጣት ይቀጣ ብለው ለመወሰን መኳንንት እንደየማዕረጋቸው እየቆሙ ከዝቅተኛው ጀምሮ እስከ ከፍተኛው ድረስ አስተያየት ሰጡ።
“ክህደት ነውና ሞት ይገባዋል!” አሉ፣ አንደኛው መኰንን።
“ግዞት ይላክ!” አሉ፣ ሌላው።
“በግርፋት ይቀየርለት!” ብለው ተቀመጡ፣ አንደኛው
“ጃንሆይ መሐሪ ናቸውና ምህረት ይደረግለትና ሹመቱን ይገፈፍ”
አሉ፣ ሌላኛው።
እንደዚህ እያለ ሁሉም ተናግረው ከጨረሱ በኋላ፣ የማሳረጊያው
ንግግር የንጉሠ ነገሥቱ በመሆኑ፣ አፈ ንጉሡ አጎንብሶ ጆሮውን
ሲሰጣቸው ሁሉም ለመስማት ጆሯቸውን ሲያቀኑ ኩቾና ተከታዮቹ
ትንፋሻቸውን ውጠው ተጠባበቁ። ይህን ሁሉ በአንክሮ የምትመለከተው ምንትዋብም ተጠባበቀች።
#ትኩሳት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...እኔና ባህራም መውጫው በር አጠገብ ያለችው ጠረጴዛ ጋ
ቁጭ ብለን ቢራ ጠጥተን ሂሳቡን ከከፈልን በኋላ፣ ባህራም
ምንም ቢመጣ ምንም፣ ከተቀመጥክበት እንዳትነሳም አለኝ
“ምን ልታረግ ነው?» ስለው
«ታያለህ» አለኝ.
ተነሳና ወደ ሽንት ቤት በኩል መራመድ ጀመረ። አንዱ
ጎረምሳ ፋሺስት ከዚያው ሲመለስ ነበር ባህራምን የገጨው፡፡ ፋሺስቴ ሳያስብበት በልማድ “Pardon” ብሎት ሲያልፍ፣ ባህራም
«አንተ!» ብሎ ጮኸበት። ፋሺስቶቹ ወሬያቸውን አቆሙ::
ካፌው በሙሉ በፀጥታ ባህራምን ማየት ጀመረ። የገጨው ፋሺስት
ወደ ባህራም ዞሯል ባህራም
«ለምን ገጨኸኝ?» አለው
ፋሺስቱ «አንተ ነህ እንጂ የገጨኸኝ አለው
«ውሽታም ፋሺስት! ውሻ ፋሺስት! ፈሪ ፋሺስት! ወንድ ከሆንክ ተከላከል። ልገርፍህ ነው» አለና ዘሎ ትግል ያዘው። የፋሺስቱ ጀርባ ወደኔ ስለነበረ፣ ባህራም ምን እንዳደረገው ለማየት
አልቻልኩም፡፡ ብቻ ምንም ያህል ሳይታገሉ ፋሺስቱ ፍስስ ብሎ ወደ
መሬት ወደቀ፡፡ ባህራም ከበላዩ እንደቆመ ዙሪያውን ተመለከተ፡፡
ከፋሺስቶቹ ማንም አልተነሳም
ባህራም ፋሺስቶቹን እያየ «ማንም ፋሽስት እንዲገጨኝ አልፈቅድለትም፡፡ ከንግዲህ ሌላ ፋሺስት የገጨኝ እንደሆነ፣ ፂሙን
ነው ምላጭለት አለና የወደቀውን ፋሺስት ተሻግሮ ወደኔ መጣ፡፡
አብረን ወጣን
(ፋሺስቶቹ እኔን ሌላ ጊዜ ቢያገኙኝ ይደበድቡኝ ይሆን? ብዬ
ትንሽ ፈራሁ፡፡ ግን ደፍረው ጥቁር ተማሪ የሚደበድቡ አልመሰለኝም፡፡ ምክንያቱም እኛ የፈረንሳይ መንግስት እንግዶች
ማለት ነን፡፡)
ባህራም ኤክስ ውስጥ አራት ቀን ቆየ፡፡ ቀን ቀን ኮሙኒስቶቹን
ሲመካክራቸው፣ እንዴት አድርገው መከላከል ፅሁፎቻቸውን እንዴት ቢያሰራጩ እንደሚሻል፣ እና ይህን የመሳሰለ ነገር ሲነግራቸው ይውላል። ማታ ማታ ፋሺስቶቹን በየጠባቡ መንገድ ሲደበድባቸው ያመሻል፡፡ በአምስተኛው ቀን ትምህርት ቤቱ ድረስ ሸኘሁት፡፡ ስለአምቧጓሮው ሲነግረኝ፣ ስለኳስ ጨዋታ የሚያወራልኝ መስሎ ተሰማኝ፡፡ በደስታ እየገነፈለ፣ ማድፊጡን መዝለሉን፣ እጁን እንደ ሰይፍ አርጎ አንገት መምታቱን፣ እንደ ዳንስ አድርጎ ገለፀልኝ
"ማኑ ይህን ሁሉ ስስራ አይቶኝ ቢሆን እንዴት ጥሩ ነበር!
ያስተማረኝን ብልሀት በሙሉ ተጠቅሜበታለሁ» አለ
«ደህና ሁን» ብዬው ወደ ኤክስ ልመለስ ስል፣ ከኪሱ አንድ
እቃ አውጥቶ አሳየኝ። የፀጉር መቁረጫ መኪና «ቶንዶዝ»፡፡
ምንድነው? አልኩት፡፡ እየሳቀ «ፋሺስቶቹ ካፌ ሂድና እቺ ነገር
ኮሙኒስት መሆንዋን ትገነዘባለህ» ብሎኝ ተለያየን ኤክስ እንደደረስኩ ፋሺሰቶቹ ካፌ ገባሁ። ብዙዎቹ እጃቸውን ወይም ጭንቅላታቸውን በፋሻ ጠምጥመዋል፡፡ ግማሾቹ ፂማቸውን ላጭተዋል። ፂማቸውን ያልላጩት ደሞ ጥቁር «ቤሬ ቆብ
አርገዋል። ለካ ባህራም ኣንድ ፋሺስት በደበደበ ቁጥር ራሱን
ወይም ፂሙን ይላጭለት ኖሯል
(እኔና ባህራም ኣንድ ግሩም የሆነ ሀራኪሪ» የተባለ የጃፓን ፊልም አይተን ነበር። እዚያ ፊልም አንዱ ጎበዝ እየዞረ የጠላቶቹን
ፀጉር ይላጫል።)
ባሀራም በሄደ በአራተኛው ቀን፣ አንዲት ኮሙኒስት ልጅ ካፌ
ቁጭ ብዬ ሳለሁ መጣችና ወደ ኤክስ አንድ ነብሰ ገዳይ መጥቷል
አለችኝ። ምን አንደሆነ ማለቴ የቱ እንደሆነ አናውቅም። ግን መምጣቱን እናውቃለን፡፡ ፋሺስቶቹ ናቸው ከማርሰይ ያስመጡት። ባህራምን ሊደበድበው ወይም ሊገድለው ነው የመጣው::»
«ፋሺስት ነው?» አልኳት
«አይደለም። የተገዛ ነብሰ ገዳይ ነው» አለችኝ
ያን ጊዜውኑ ሲልቪ ቤት ሄድኩ። በአቶቡስ እንዳልሄድ
ምናልባት ፋሺስቶቹ ይከታተሉኛልና፡ ካንቺ ጋር ለሽርሽር የምንወጣ አስመስለን እንሂድ አልኳት።በመኪናዋ ሄድን። ለባህራም ነገርኩት።
ሲልቪ ቤቷ ወስዳን እራት በላን። ከዚያ ሶስታችንም ሄደን
ፋሺስቶቹ ካፌ ገብተን ሁለት ሰአት ያህል አሳለፍን። ይህን ሁሉ
ጊዜ ባህራምና ሲልቪ ያወሩ፣ ይቀልዱ፣ ይስቁ ነበር፡፡ እኔ ግን
ምንም ያህል አላወራሁም። ለባህራም ፈርቼለት ነበር፡፡ ሰውየው የቱ እንደሆነ ብናውቅ እንኳ ለመከላከል እንሞክር ነበር። አሁን ግን ከማንኛውም አቅጣጫ ጦር ሊወረወርበት በሚችልበት
ውስጥ፣ ባህራም ብቻውን የሚራመድ መስሎ ተሰማኝ
አብሬያቸው ባለማውራቴ፣ የኔ ፍርሀት ቀስ እያለ ወደ ሲልቫ
ተላለፈባት
“ፈራሁ። በጣም ፈራሁ» አለች
ባህራም «ምን ያስፈራሻል?» አላት፡፡ ግን ድምፁ እንደ ድሮ
ልዝብ መሆኑ ቀርቶ፣ ትንሽ እሾህም ሆኗል
«ማን እንደሆነ ወይም የት እንደሆነ አናውቅም፡፡ አንድ
ብቻውን መሆኑን እንኳ በእርግጥ አናውቅም፡፡»
«እና?»
አንድ ነገር ብትሆንስ? ብትሞትስ?» አለችው
እኔ? ትቀልጂያለሽ? የኛ ቤተሰብ”ኮ እስኪጃጅ ካላረጀ
አይሞትም፡፡ የኔ ወንድ አያት፣ ያባቴ አባት፣ በዘጠና ሰባት
አመታቸው ብቻቸውን ሜካ መዲና ደርሰው ተመልስዋል። ታድያ
እንደተመለሱ የቤታችን ጣራ ዝናብ ማስገባት ሲጀምር ጊዜ፣
ሊያበጁት በመስሳል ወጡ። አበጅተውት ሲወርዱ ከመሰላል ወደቁና እግራቸው ወለም ብሏቸው ሁለት ሳምንት ሙሉ እንዲተኙ ሀኪም አዘዛቸው:: ታድያ ሁለት ሳምንት እንዴት ይለፍ? ውሽማቸው ናፈቀቻቸው። እና ገና አንድ ሳምንት ሳይተኙ፣ ሌሊት ጠፍተው ውሽማቸው ቤት ሄዱ። መኝታ ቤቷ በመስኮት እገባለሁ ሲሉ ባልየው በጥይት ልባቸውን አፈረሰላቸው:: ስንቀብራቸው የኔ አባት
«አይ አባባ! አይ አባባ! እኛ ያረጀነው እያለን አንተ ወጣት
ተቀጨህ!» ብሎ አለቀሰ፡»
ስንስቅ ሲልቪ በጆሮዬ እኔ ፍርሀት አቁነጠነጠኝ፡፡ ሽንቴ መጣ» ብላኝ ወደ ሽንት ቤት ሄደች
ባህራምን «የጀምሺድን የሚመስል ታሪክ ከየት አመጣህ?» አልኩት
( ከጀምሺድ ነዋ!» አለኝ «ስማኝ፡፡ እንድ ነገር አርግልኝ።
እዚያው ትደር፡፡ እና ነገ በሌሊት ተነስቶ ማርሰይ እንዲወስዳትና
ለአንድ ሳምንት ያህል ተደብቀው እንዲቆዩ ንገረው::
ቀፈፈኝ። በባህራም ትእዛዝ ኒኮልን ጀምሺድ ቤት ወስጄ ለጀምሺድ ላስረክበው ለአንድ ሳምንት ሙሉ! በጣም ቀፈፈኝ፡፡ ግን
ምን ማድረግ እችላለሁ?
አንተም ይህን ሰሞን ተጠንቀቅ። ማታ ብቻህን አትውጣ»
አለኝ። ሲጋራ አቀጣጠለ። እጁ ትንሽ ትንሽ ይንቀጠቀጣል። ፍርሀት አሳደረብኝ
ሲልቪ ተመለሰች። ደህና እደሩ ብያቸው ሄድኩ ኒኮልን ቤቷ እገኘኋት። ጀምሺድ ቤት ስንሄድ አጣነው፡፡ ቤቱ ቁልፍ ነው። ካፌ ዶርቢቴል ሄደን ጠያየቅን፡፡ ተካ፣ ጀምሺድና ሉልሰገድ ኒስ ሄደዋል አሉን። ኒኮልና እኔ የመጨረሻውን የማታ አቶቡስ ተሳፍረን ማርሰይ ወረድን፡፡ አንድ ወሻቃ ቦታ ሆቴል
አገኘን። ባለ ሁለት አልጋ ክፍል ተከራየን። ሁለታችንም ለባህራም
ሰግተናል። አንቅልፋችን እንደማይመጣ ግልጽ ነው:: አንድ ቆሻሻ ብጤ ጭር ያለ ካፌ ገብተን ከልቫዶስ እየጠጣን፣ እያወራን፣
እየተያየን ሳቃችን እየመጣ፤ እየተሳሳቅን፣ ድንገት ሳቃችንን
አቋርጠን በፀጥታ እየተያየን፣ ስንተያይ ኒኮል በሚያስጐመጅ አኳኋን እየቀላች፣ እየቀላች፣ እየጠጣን እያወራን፤ ከአንድ ሰእት በላይ አሳለፍን፡ ሰከርን፡፡ የተረፈንን ግማሽ ጠርሙስ ካልቫዶስ ይዘነው ሞቃት ሰማይ መሀል
ሆቴላችን ስንደርስ፤ እንዳንተያይ መብራቱን አጥፍተን፣
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር
...እኔና ባህራም መውጫው በር አጠገብ ያለችው ጠረጴዛ ጋ
ቁጭ ብለን ቢራ ጠጥተን ሂሳቡን ከከፈልን በኋላ፣ ባህራም
ምንም ቢመጣ ምንም፣ ከተቀመጥክበት እንዳትነሳም አለኝ
“ምን ልታረግ ነው?» ስለው
«ታያለህ» አለኝ.
ተነሳና ወደ ሽንት ቤት በኩል መራመድ ጀመረ። አንዱ
ጎረምሳ ፋሺስት ከዚያው ሲመለስ ነበር ባህራምን የገጨው፡፡ ፋሺስቴ ሳያስብበት በልማድ “Pardon” ብሎት ሲያልፍ፣ ባህራም
«አንተ!» ብሎ ጮኸበት። ፋሺስቶቹ ወሬያቸውን አቆሙ::
ካፌው በሙሉ በፀጥታ ባህራምን ማየት ጀመረ። የገጨው ፋሺስት
ወደ ባህራም ዞሯል ባህራም
«ለምን ገጨኸኝ?» አለው
ፋሺስቱ «አንተ ነህ እንጂ የገጨኸኝ አለው
«ውሽታም ፋሺስት! ውሻ ፋሺስት! ፈሪ ፋሺስት! ወንድ ከሆንክ ተከላከል። ልገርፍህ ነው» አለና ዘሎ ትግል ያዘው። የፋሺስቱ ጀርባ ወደኔ ስለነበረ፣ ባህራም ምን እንዳደረገው ለማየት
አልቻልኩም፡፡ ብቻ ምንም ያህል ሳይታገሉ ፋሺስቱ ፍስስ ብሎ ወደ
መሬት ወደቀ፡፡ ባህራም ከበላዩ እንደቆመ ዙሪያውን ተመለከተ፡፡
ከፋሺስቶቹ ማንም አልተነሳም
ባህራም ፋሺስቶቹን እያየ «ማንም ፋሽስት እንዲገጨኝ አልፈቅድለትም፡፡ ከንግዲህ ሌላ ፋሺስት የገጨኝ እንደሆነ፣ ፂሙን
ነው ምላጭለት አለና የወደቀውን ፋሺስት ተሻግሮ ወደኔ መጣ፡፡
አብረን ወጣን
(ፋሺስቶቹ እኔን ሌላ ጊዜ ቢያገኙኝ ይደበድቡኝ ይሆን? ብዬ
ትንሽ ፈራሁ፡፡ ግን ደፍረው ጥቁር ተማሪ የሚደበድቡ አልመሰለኝም፡፡ ምክንያቱም እኛ የፈረንሳይ መንግስት እንግዶች
ማለት ነን፡፡)
ባህራም ኤክስ ውስጥ አራት ቀን ቆየ፡፡ ቀን ቀን ኮሙኒስቶቹን
ሲመካክራቸው፣ እንዴት አድርገው መከላከል ፅሁፎቻቸውን እንዴት ቢያሰራጩ እንደሚሻል፣ እና ይህን የመሳሰለ ነገር ሲነግራቸው ይውላል። ማታ ማታ ፋሺስቶቹን በየጠባቡ መንገድ ሲደበድባቸው ያመሻል፡፡ በአምስተኛው ቀን ትምህርት ቤቱ ድረስ ሸኘሁት፡፡ ስለአምቧጓሮው ሲነግረኝ፣ ስለኳስ ጨዋታ የሚያወራልኝ መስሎ ተሰማኝ፡፡ በደስታ እየገነፈለ፣ ማድፊጡን መዝለሉን፣ እጁን እንደ ሰይፍ አርጎ አንገት መምታቱን፣ እንደ ዳንስ አድርጎ ገለፀልኝ
"ማኑ ይህን ሁሉ ስስራ አይቶኝ ቢሆን እንዴት ጥሩ ነበር!
ያስተማረኝን ብልሀት በሙሉ ተጠቅሜበታለሁ» አለ
«ደህና ሁን» ብዬው ወደ ኤክስ ልመለስ ስል፣ ከኪሱ አንድ
እቃ አውጥቶ አሳየኝ። የፀጉር መቁረጫ መኪና «ቶንዶዝ»፡፡
ምንድነው? አልኩት፡፡ እየሳቀ «ፋሺስቶቹ ካፌ ሂድና እቺ ነገር
ኮሙኒስት መሆንዋን ትገነዘባለህ» ብሎኝ ተለያየን ኤክስ እንደደረስኩ ፋሺሰቶቹ ካፌ ገባሁ። ብዙዎቹ እጃቸውን ወይም ጭንቅላታቸውን በፋሻ ጠምጥመዋል፡፡ ግማሾቹ ፂማቸውን ላጭተዋል። ፂማቸውን ያልላጩት ደሞ ጥቁር «ቤሬ ቆብ
አርገዋል። ለካ ባህራም ኣንድ ፋሺስት በደበደበ ቁጥር ራሱን
ወይም ፂሙን ይላጭለት ኖሯል
(እኔና ባህራም ኣንድ ግሩም የሆነ ሀራኪሪ» የተባለ የጃፓን ፊልም አይተን ነበር። እዚያ ፊልም አንዱ ጎበዝ እየዞረ የጠላቶቹን
ፀጉር ይላጫል።)
ባሀራም በሄደ በአራተኛው ቀን፣ አንዲት ኮሙኒስት ልጅ ካፌ
ቁጭ ብዬ ሳለሁ መጣችና ወደ ኤክስ አንድ ነብሰ ገዳይ መጥቷል
አለችኝ። ምን አንደሆነ ማለቴ የቱ እንደሆነ አናውቅም። ግን መምጣቱን እናውቃለን፡፡ ፋሺስቶቹ ናቸው ከማርሰይ ያስመጡት። ባህራምን ሊደበድበው ወይም ሊገድለው ነው የመጣው::»
«ፋሺስት ነው?» አልኳት
«አይደለም። የተገዛ ነብሰ ገዳይ ነው» አለችኝ
ያን ጊዜውኑ ሲልቪ ቤት ሄድኩ። በአቶቡስ እንዳልሄድ
ምናልባት ፋሺስቶቹ ይከታተሉኛልና፡ ካንቺ ጋር ለሽርሽር የምንወጣ አስመስለን እንሂድ አልኳት።በመኪናዋ ሄድን። ለባህራም ነገርኩት።
ሲልቪ ቤቷ ወስዳን እራት በላን። ከዚያ ሶስታችንም ሄደን
ፋሺስቶቹ ካፌ ገብተን ሁለት ሰአት ያህል አሳለፍን። ይህን ሁሉ
ጊዜ ባህራምና ሲልቪ ያወሩ፣ ይቀልዱ፣ ይስቁ ነበር፡፡ እኔ ግን
ምንም ያህል አላወራሁም። ለባህራም ፈርቼለት ነበር፡፡ ሰውየው የቱ እንደሆነ ብናውቅ እንኳ ለመከላከል እንሞክር ነበር። አሁን ግን ከማንኛውም አቅጣጫ ጦር ሊወረወርበት በሚችልበት
ውስጥ፣ ባህራም ብቻውን የሚራመድ መስሎ ተሰማኝ
አብሬያቸው ባለማውራቴ፣ የኔ ፍርሀት ቀስ እያለ ወደ ሲልቫ
ተላለፈባት
“ፈራሁ። በጣም ፈራሁ» አለች
ባህራም «ምን ያስፈራሻል?» አላት፡፡ ግን ድምፁ እንደ ድሮ
ልዝብ መሆኑ ቀርቶ፣ ትንሽ እሾህም ሆኗል
«ማን እንደሆነ ወይም የት እንደሆነ አናውቅም፡፡ አንድ
ብቻውን መሆኑን እንኳ በእርግጥ አናውቅም፡፡»
«እና?»
አንድ ነገር ብትሆንስ? ብትሞትስ?» አለችው
እኔ? ትቀልጂያለሽ? የኛ ቤተሰብ”ኮ እስኪጃጅ ካላረጀ
አይሞትም፡፡ የኔ ወንድ አያት፣ ያባቴ አባት፣ በዘጠና ሰባት
አመታቸው ብቻቸውን ሜካ መዲና ደርሰው ተመልስዋል። ታድያ
እንደተመለሱ የቤታችን ጣራ ዝናብ ማስገባት ሲጀምር ጊዜ፣
ሊያበጁት በመስሳል ወጡ። አበጅተውት ሲወርዱ ከመሰላል ወደቁና እግራቸው ወለም ብሏቸው ሁለት ሳምንት ሙሉ እንዲተኙ ሀኪም አዘዛቸው:: ታድያ ሁለት ሳምንት እንዴት ይለፍ? ውሽማቸው ናፈቀቻቸው። እና ገና አንድ ሳምንት ሳይተኙ፣ ሌሊት ጠፍተው ውሽማቸው ቤት ሄዱ። መኝታ ቤቷ በመስኮት እገባለሁ ሲሉ ባልየው በጥይት ልባቸውን አፈረሰላቸው:: ስንቀብራቸው የኔ አባት
«አይ አባባ! አይ አባባ! እኛ ያረጀነው እያለን አንተ ወጣት
ተቀጨህ!» ብሎ አለቀሰ፡»
ስንስቅ ሲልቪ በጆሮዬ እኔ ፍርሀት አቁነጠነጠኝ፡፡ ሽንቴ መጣ» ብላኝ ወደ ሽንት ቤት ሄደች
ባህራምን «የጀምሺድን የሚመስል ታሪክ ከየት አመጣህ?» አልኩት
( ከጀምሺድ ነዋ!» አለኝ «ስማኝ፡፡ እንድ ነገር አርግልኝ።
እዚያው ትደር፡፡ እና ነገ በሌሊት ተነስቶ ማርሰይ እንዲወስዳትና
ለአንድ ሳምንት ያህል ተደብቀው እንዲቆዩ ንገረው::
ቀፈፈኝ። በባህራም ትእዛዝ ኒኮልን ጀምሺድ ቤት ወስጄ ለጀምሺድ ላስረክበው ለአንድ ሳምንት ሙሉ! በጣም ቀፈፈኝ፡፡ ግን
ምን ማድረግ እችላለሁ?
አንተም ይህን ሰሞን ተጠንቀቅ። ማታ ብቻህን አትውጣ»
አለኝ። ሲጋራ አቀጣጠለ። እጁ ትንሽ ትንሽ ይንቀጠቀጣል። ፍርሀት አሳደረብኝ
ሲልቪ ተመለሰች። ደህና እደሩ ብያቸው ሄድኩ ኒኮልን ቤቷ እገኘኋት። ጀምሺድ ቤት ስንሄድ አጣነው፡፡ ቤቱ ቁልፍ ነው። ካፌ ዶርቢቴል ሄደን ጠያየቅን፡፡ ተካ፣ ጀምሺድና ሉልሰገድ ኒስ ሄደዋል አሉን። ኒኮልና እኔ የመጨረሻውን የማታ አቶቡስ ተሳፍረን ማርሰይ ወረድን፡፡ አንድ ወሻቃ ቦታ ሆቴል
አገኘን። ባለ ሁለት አልጋ ክፍል ተከራየን። ሁለታችንም ለባህራም
ሰግተናል። አንቅልፋችን እንደማይመጣ ግልጽ ነው:: አንድ ቆሻሻ ብጤ ጭር ያለ ካፌ ገብተን ከልቫዶስ እየጠጣን፣ እያወራን፣
እየተያየን ሳቃችን እየመጣ፤ እየተሳሳቅን፣ ድንገት ሳቃችንን
አቋርጠን በፀጥታ እየተያየን፣ ስንተያይ ኒኮል በሚያስጐመጅ አኳኋን እየቀላች፣ እየቀላች፣ እየጠጣን እያወራን፤ ከአንድ ሰእት በላይ አሳለፍን፡ ሰከርን፡፡ የተረፈንን ግማሽ ጠርሙስ ካልቫዶስ ይዘነው ሞቃት ሰማይ መሀል
ሆቴላችን ስንደርስ፤ እንዳንተያይ መብራቱን አጥፍተን፣
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት እንደዚያ ልብ ዘርታ ትጫወት የነበረችው ሴትዮ አሁን በድንገት ተለዋወጣ ዝልፍልፍ አለች::
«ያንተ ያለህ! ምነው ፋንቲን፤ ምን ነካሽ?» ሲል መሴይ ማንደላይን
ጠየቃት::
መልስ አልሰጠችውም:: አፍጥጣ ትመለከትበት ከነበረው አቅጣጫ
ዓይንዋን አላዞረችም:: በአንድ እጅዋ የመሴይ ማንደላይንን እጅ ጨብጣ በሌላው እጅዋ ወደኋላው እንዲያይ አመለከተችው::
ፊቱን አዞረ:: ገናቬርን ከዚያ ቆሞ አየው::
ከዚያ በኋላ ምን እንደሆነ እንመልከት::
በጣም ከመሸ ነበር መሴይ ማንደላይን ፍርድ ቤቱን ለቅቆ የወጣው::ወዲያው እንደወጣ ከበራፍ ይጠብቀው በነበረው ሠረገላ በቀጥታ ወደ ቤቱ
ተመለሰ፡፡ ሊነጋጋ ሲል ነበር ሞንቴስ ሰር ሞንቴስ ከተባለ ሥፍራ የደረሰው::ከዚያም እንደደረሰ ለመሴይ ላፌት ደብዳቤ ከላከ በኋላ ነበር ፋንቲንን
ለመጠየቅ ወደ ተኛችበት ክፍል የሄደው::
ፍርድ ቤቱ ሻምፕማቲዩን በነፃ ካሰናበተ በኋላ ሕግ አስከባሪውና
ዳኞቹ ተመካከሩ፡፡ የተመካከሩት መሴይ ማንደላይንን ያሳሰሩት ወይም አያሳስሩት እንደሆነ ነበር፡፡ መታሰር እንዳለበት ወስነው በአለበት እንዲያዝ ትእዛዝ ሰጡ፡፡ ሕግ አስከባሪው በአስቸኳይ ወደ ከተማው ፖሊስ አዛዥ
ወደ ዣቬር ወዲያውኑ መልክተኛ ልኮ ከንቲባውን እንዲይዝ ትእዛዝ
አስተላለፈለት::
ዣቬር ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነሳ መልእክተኛው ደርሶ ትእዛዙን
ሰጠው:: መልእክተኛው የፖሊስ አባል ሲሆን ይህም መለዮ ለባሽ ፍርድ ቤቱ ውስጥ ምን እንደተከሰተ ለዣቬር ባጭሩ አስረዳው::
የትእዛዙ ፍሬ አሳብ «የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ከንቲባ መሴይ ማንደላይን ከእስር ቤት ያመለጠው ዣን ቫልዣ መሆኑ ስለታወቀ የፖሊሱ ኣዛዥ
በቁጥጥር ስር እንዲያውለው ፍርድ ቤቱ አዟል» የሚል ነበር፡፡
ዣቬር አንድ የአስር አለቃና አራት ወታደሮችን አስከትሎ ከከንቲባው
ቤት ሄደ:: መሴይ ማንደላይን ፋንቲን ከነበረችበት ክፍል መሆኑን ጠይቆ ከተረዳ በኋላ በቀጥታ ወደዚያ ሄዶ በሩ ላይ ተሰክቶ በነበረው ቁልፍ በሩን ቀስ ብሎ ከፍቶ ገባ፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ በሩን ከፈተው እንጂ ወደ ውስጥ ለመግባት
አልደፈረም:: ካፖርቱን እስከ አንገቱ ግጥም አድርጎ ቆልፎ ቆቡን አጥልቆአል፡፡ወደ ክፍሉ ያስገባው መላ ሰውነቱን ሳይሆን አንገቱን ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም
በሩ ስለተከፈተ ማን እንደሆነ በግልጽ ይታያል፡፡ እንደዚያ ሆኖ ምናልባት ለአንድ ደቂቃ ያህል ዝም ብሎ ቆሞ ይሆናል:: ይሄኔ ነው ፋንቲን አይታው
ለመሴይ ማንደላይን የጠቆመችው፡፡ ሁለቱ ተያዩ:: ዣቬር አልተነቃነቀም:: ያ ግዙፍ ሰውነቱ እንኳን ካፖርት ደርቦበት እንዲሁም ይከብዳል፡፡ ፊቱን አጠቋቁሮ ፧ ጥርሱን አግጥጦና
ዓይኑን አፍጥጦ «አገኘሁህ» በማለት ሲያይ በጣም ያስፈራል፡፡
በመጨረሻ ዣን ቫልዣን በመያዙ አካሉ ውስጥ የነበረው ያንን ሰው
አሳድዶ የመያዝ ጽኑ ፍላጎትና ምኞት ተጎልጉሎ ወጥቶ ገጹ ላይ ታየ:: «ዛሬስ ድል መታሁ» የሚለው ደስታው ደግሞ ከዚያች ከጠባብ ግምባሩ ላይ በጉልህ ወጣ፡፡
ዣቬር በዚያች ቅጽበት መንግሥተ ሰማይ ገብቷል፡፡ የዣቬርን
ቁመናና ሁኔታ ረስተን የዘወትር ፍላጎቱና ምኞቱ ምን እንደሆነ ብናጤን «ትክክለኛ ፍርድ ፤ እውነትና ብርሃን የክፉ ሥራ አጥፊዎች ናቸው የሚል ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ እነዚህም የሕግ፣ የሥልጣን፣ የሕሊናና
የመሳሰሉት የበቀል መሣሪያዎች ናቸው፡፡ ከዚያ ክፍል ውስጥ ቆሞ : የሚታየው ይህን ለማስፈጸም ነበር፡፡ በእርሱ ዓይን ርህራሄ፣ ፍርሃትና ይሉኝታ የሕግ ጠላቶችና የትክክለኛ ፍርድ እንቅፋቶች ሲሆኑ ይህ ሰው
ፍርድን ላለማዛባት ምንም ነገር ያደርጋል፡፡ የዘወትር እምነቱ ከህብረተሰብ መካከል ቅጥፈት፣ ተንኮልና ወንጀል ጨርሶ ማስወገድ ሲሆን ይህን
ከማስፈጸም ወደኋላ ስለማይል «የነገሮች መነሻዎች ምንድናቸው» የሚል አስተያየት አያውቅም:: ዓላማውና ምኞቱ ሕግን ማስከበር ነው:: ይህ
እምነቱ ነው ፊቱ ላይ እየታየ ገና ሲመለከቱት የሚዋጋ በሬ ያስመሰለው።
መሴይ ማንደላይን ከመንጋጋው ፈልቅቆ ካወጣት ወዲህ ፋንቲን
ዣቬርን አላየችውም፡፡ ስለዚህ በጠዋት የመጣው እርስዋን ለመያዝ እንጂ ለሌላ ነገር ነው ብላ አልገመተችም:: ፊቱ ያስጠላታል፡፡ የእርሱን ፊት
ለረጅም ጊዜ ካየች ሞትዋ የተቃረበ ይመስላታል:: ስለዚህ ፊትዋን በእጅዋ ሽፈነችው::
«መሴይ ማንደላይን ያድኑኝ፧ ከዚህ ጉድ ያወጡኝ» ስትል ጮኸች፡፡
«አይዞሽ፣ አንቺን ሳይሆን እኔን ፍለጋ ነው የመጣው::»
ከዚያም ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ምን እንደምትፈልግ አውቃለሁ
አለው::
ዣቬር «ፈጠን በል» ሲል መለሰ፡፡
ዣቬር ይህን ሲናገር ከቆመበት አልተነቃነቀም:: ግን ዘወትር
የጠላቸውን በሚያይበት ዓይን ነበር ዣን ቫልዣን ያየው:: ከሁለት ወር በፊት ፋንቲንን ያያት ልክ እንዳሁኑ አጥንት ሰርስሮ በሚገባ ዓይነት አስተያየተ ነበር፡፡ ለዚህ ነው አሁንም የፈራችውና «አድነኝ ብላ» የጮኸችው::
ዣቬር እንድ እርምጃ ወደፊት ተራመደ::
«እንሂድ፣ ምነው ወደኋላ!» ሲል ጠየቀ፡፡ ያቺ የተከፋች ሴት ኣካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሴርዋና ከንቲባው መሆናቸውን ተገነዘበች፡፡
ይህ ሰው የመጣው «እኔን ሊወስድ እንጂ ለሌላ ሰው አልመጣም» ብላ ስለደመደመች ሰውነትዋ ተንቀጠቀጠ፡፡ ሆኖም ወዲያው ጨርሶ የማይታሰብ
ነገር አየች:: ያየችው ነገር በእውን ሳይሆን በቅዠት እንኳን ሊታያት
የማይችል እንደሆነ ገመተች::
የፖሊሶ አዛኝዥ ዣቬር የመሴይ ማንደላይንን ማንቁርት ይዞ ሲጎትትና መሴይ ማንደላይን አንገቱን ሲደፋ ተመለከተች:: ዓለም ከፊትዋ የተደፋ
መሰላት::
ዣቬር ሰላሣ ሁለት ጥርሶቹን በመሉ እያሳየ ከት ብሎ ሳቀ::
«የእኛ ከንቲባ!» በማለት በይበልጥ አንቆ ያዘው::
መሴይ ማንደላይን አንገቱን ለማስለቀቅ አልሞከረም፡፡ ግን «ዣቬር» ሲል ተናገረ::
ዣቬር ጣልቃ በመግባት አቋረጠው:: ክቡር የፖሊስ አዛዥ ብለህ ጥራኝ» አለው::
«ክቡር» አለ ዣን ቫልዣ ፧ ብቻችንን ብንሆን አንድ የምጠይቅህ ነገር
ነበረኝ::
«ጮክ በል፣ ድምፅህን ከፍ ኣድርገህ ተናገር:: ሰዎች እኔን ሲያናግሩ ጮክ እያሉ ነው የሚያነጋግሩኝ» አለ ዣቬር፡፡
ድምፁን ዝቅ አድርጎ ዣን ቫልዣ ንግግሩን ቀጠለ::
«አንተን በግል የምለምንህ ጉዳይ አለኝ፡፡››
‹‹ጮክ ብለህ ተናገር ብዬህ እኮ ነበር፡፡»
«ግን የምነግርህ ነገር እኔና አንተ እንጂ ሌላ ሰው መስማት ስለሌለበት ነው::
“ጉዳዩ መሰለህ፤ በአንተ ጉዳይ እኔን ምን አስጨነቀኝ፣ አልሰማም::
ዣን ቫልዣ ጠጋ ብሎ በችኮላ አሁንም ድምፁን ዝቅ እድርጎ
የሚከተለውን ተናገረ::
« ሦስት ቀን ብቻ ስጠኝ! የዚህች የተከፋች ሴት ልጅ ሄጄ ላምጣላት::የሚያስፈልገውን ወጪ በሙሉ እኔ እከፍላለሁ:: ከፈለግክ አብረን ልንሄድ እንችላለን፡፡
«በእኔ ላይ ነው የምታሾፈው» አለ ዣቬር፡፡ «እስከዚህ ሞኝ
አትመሰለኝም ነበር:: ሦስት ቀን ስጠኝና የዚህችን ሴት ልጅ ላምጣ' ትለኛለህ:: በጣም ታስቃለህ፡፡»
የፋንቲን ሰውነት ተንቀጠቀጠ፡፡
«ልጄን» ስትል ጮኸች፡፡ «ልጄ ዘንድ ሊሄዱ ነዋ! ወይኔ ልጄ፧
አልመጣችም ማለት ነዋ! ሲስተር ይንገሩኝ፤ ልጄ የት ናት? መሴይ
ማንደላይን፤ ክቡር ከንቲባ ልጄን እፈልጋታለሁ!»
ዣቬር ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት መሬቱን በጫማው ረገጠው::
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት እንደዚያ ልብ ዘርታ ትጫወት የነበረችው ሴትዮ አሁን በድንገት ተለዋወጣ ዝልፍልፍ አለች::
«ያንተ ያለህ! ምነው ፋንቲን፤ ምን ነካሽ?» ሲል መሴይ ማንደላይን
ጠየቃት::
መልስ አልሰጠችውም:: አፍጥጣ ትመለከትበት ከነበረው አቅጣጫ
ዓይንዋን አላዞረችም:: በአንድ እጅዋ የመሴይ ማንደላይንን እጅ ጨብጣ በሌላው እጅዋ ወደኋላው እንዲያይ አመለከተችው::
ፊቱን አዞረ:: ገናቬርን ከዚያ ቆሞ አየው::
ከዚያ በኋላ ምን እንደሆነ እንመልከት::
በጣም ከመሸ ነበር መሴይ ማንደላይን ፍርድ ቤቱን ለቅቆ የወጣው::ወዲያው እንደወጣ ከበራፍ ይጠብቀው በነበረው ሠረገላ በቀጥታ ወደ ቤቱ
ተመለሰ፡፡ ሊነጋጋ ሲል ነበር ሞንቴስ ሰር ሞንቴስ ከተባለ ሥፍራ የደረሰው::ከዚያም እንደደረሰ ለመሴይ ላፌት ደብዳቤ ከላከ በኋላ ነበር ፋንቲንን
ለመጠየቅ ወደ ተኛችበት ክፍል የሄደው::
ፍርድ ቤቱ ሻምፕማቲዩን በነፃ ካሰናበተ በኋላ ሕግ አስከባሪውና
ዳኞቹ ተመካከሩ፡፡ የተመካከሩት መሴይ ማንደላይንን ያሳሰሩት ወይም አያሳስሩት እንደሆነ ነበር፡፡ መታሰር እንዳለበት ወስነው በአለበት እንዲያዝ ትእዛዝ ሰጡ፡፡ ሕግ አስከባሪው በአስቸኳይ ወደ ከተማው ፖሊስ አዛዥ
ወደ ዣቬር ወዲያውኑ መልክተኛ ልኮ ከንቲባውን እንዲይዝ ትእዛዝ
አስተላለፈለት::
ዣቬር ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነሳ መልእክተኛው ደርሶ ትእዛዙን
ሰጠው:: መልእክተኛው የፖሊስ አባል ሲሆን ይህም መለዮ ለባሽ ፍርድ ቤቱ ውስጥ ምን እንደተከሰተ ለዣቬር ባጭሩ አስረዳው::
የትእዛዙ ፍሬ አሳብ «የሞንቴስ ሱር ሞንቴስ ከንቲባ መሴይ ማንደላይን ከእስር ቤት ያመለጠው ዣን ቫልዣ መሆኑ ስለታወቀ የፖሊሱ ኣዛዥ
በቁጥጥር ስር እንዲያውለው ፍርድ ቤቱ አዟል» የሚል ነበር፡፡
ዣቬር አንድ የአስር አለቃና አራት ወታደሮችን አስከትሎ ከከንቲባው
ቤት ሄደ:: መሴይ ማንደላይን ፋንቲን ከነበረችበት ክፍል መሆኑን ጠይቆ ከተረዳ በኋላ በቀጥታ ወደዚያ ሄዶ በሩ ላይ ተሰክቶ በነበረው ቁልፍ በሩን ቀስ ብሎ ከፍቶ ገባ፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ በሩን ከፈተው እንጂ ወደ ውስጥ ለመግባት
አልደፈረም:: ካፖርቱን እስከ አንገቱ ግጥም አድርጎ ቆልፎ ቆቡን አጥልቆአል፡፡ወደ ክፍሉ ያስገባው መላ ሰውነቱን ሳይሆን አንገቱን ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም
በሩ ስለተከፈተ ማን እንደሆነ በግልጽ ይታያል፡፡ እንደዚያ ሆኖ ምናልባት ለአንድ ደቂቃ ያህል ዝም ብሎ ቆሞ ይሆናል:: ይሄኔ ነው ፋንቲን አይታው
ለመሴይ ማንደላይን የጠቆመችው፡፡ ሁለቱ ተያዩ:: ዣቬር አልተነቃነቀም:: ያ ግዙፍ ሰውነቱ እንኳን ካፖርት ደርቦበት እንዲሁም ይከብዳል፡፡ ፊቱን አጠቋቁሮ ፧ ጥርሱን አግጥጦና
ዓይኑን አፍጥጦ «አገኘሁህ» በማለት ሲያይ በጣም ያስፈራል፡፡
በመጨረሻ ዣን ቫልዣን በመያዙ አካሉ ውስጥ የነበረው ያንን ሰው
አሳድዶ የመያዝ ጽኑ ፍላጎትና ምኞት ተጎልጉሎ ወጥቶ ገጹ ላይ ታየ:: «ዛሬስ ድል መታሁ» የሚለው ደስታው ደግሞ ከዚያች ከጠባብ ግምባሩ ላይ በጉልህ ወጣ፡፡
ዣቬር በዚያች ቅጽበት መንግሥተ ሰማይ ገብቷል፡፡ የዣቬርን
ቁመናና ሁኔታ ረስተን የዘወትር ፍላጎቱና ምኞቱ ምን እንደሆነ ብናጤን «ትክክለኛ ፍርድ ፤ እውነትና ብርሃን የክፉ ሥራ አጥፊዎች ናቸው የሚል ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ እነዚህም የሕግ፣ የሥልጣን፣ የሕሊናና
የመሳሰሉት የበቀል መሣሪያዎች ናቸው፡፡ ከዚያ ክፍል ውስጥ ቆሞ : የሚታየው ይህን ለማስፈጸም ነበር፡፡ በእርሱ ዓይን ርህራሄ፣ ፍርሃትና ይሉኝታ የሕግ ጠላቶችና የትክክለኛ ፍርድ እንቅፋቶች ሲሆኑ ይህ ሰው
ፍርድን ላለማዛባት ምንም ነገር ያደርጋል፡፡ የዘወትር እምነቱ ከህብረተሰብ መካከል ቅጥፈት፣ ተንኮልና ወንጀል ጨርሶ ማስወገድ ሲሆን ይህን
ከማስፈጸም ወደኋላ ስለማይል «የነገሮች መነሻዎች ምንድናቸው» የሚል አስተያየት አያውቅም:: ዓላማውና ምኞቱ ሕግን ማስከበር ነው:: ይህ
እምነቱ ነው ፊቱ ላይ እየታየ ገና ሲመለከቱት የሚዋጋ በሬ ያስመሰለው።
መሴይ ማንደላይን ከመንጋጋው ፈልቅቆ ካወጣት ወዲህ ፋንቲን
ዣቬርን አላየችውም፡፡ ስለዚህ በጠዋት የመጣው እርስዋን ለመያዝ እንጂ ለሌላ ነገር ነው ብላ አልገመተችም:: ፊቱ ያስጠላታል፡፡ የእርሱን ፊት
ለረጅም ጊዜ ካየች ሞትዋ የተቃረበ ይመስላታል:: ስለዚህ ፊትዋን በእጅዋ ሽፈነችው::
«መሴይ ማንደላይን ያድኑኝ፧ ከዚህ ጉድ ያወጡኝ» ስትል ጮኸች፡፡
«አይዞሽ፣ አንቺን ሳይሆን እኔን ፍለጋ ነው የመጣው::»
ከዚያም ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ምን እንደምትፈልግ አውቃለሁ
አለው::
ዣቬር «ፈጠን በል» ሲል መለሰ፡፡
ዣቬር ይህን ሲናገር ከቆመበት አልተነቃነቀም:: ግን ዘወትር
የጠላቸውን በሚያይበት ዓይን ነበር ዣን ቫልዣን ያየው:: ከሁለት ወር በፊት ፋንቲንን ያያት ልክ እንዳሁኑ አጥንት ሰርስሮ በሚገባ ዓይነት አስተያየተ ነበር፡፡ ለዚህ ነው አሁንም የፈራችውና «አድነኝ ብላ» የጮኸችው::
ዣቬር እንድ እርምጃ ወደፊት ተራመደ::
«እንሂድ፣ ምነው ወደኋላ!» ሲል ጠየቀ፡፡ ያቺ የተከፋች ሴት ኣካባቢዋን ቃኘች፡፡ ከክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሴርዋና ከንቲባው መሆናቸውን ተገነዘበች፡፡
ይህ ሰው የመጣው «እኔን ሊወስድ እንጂ ለሌላ ሰው አልመጣም» ብላ ስለደመደመች ሰውነትዋ ተንቀጠቀጠ፡፡ ሆኖም ወዲያው ጨርሶ የማይታሰብ
ነገር አየች:: ያየችው ነገር በእውን ሳይሆን በቅዠት እንኳን ሊታያት
የማይችል እንደሆነ ገመተች::
የፖሊሶ አዛኝዥ ዣቬር የመሴይ ማንደላይንን ማንቁርት ይዞ ሲጎትትና መሴይ ማንደላይን አንገቱን ሲደፋ ተመለከተች:: ዓለም ከፊትዋ የተደፋ
መሰላት::
ዣቬር ሰላሣ ሁለት ጥርሶቹን በመሉ እያሳየ ከት ብሎ ሳቀ::
«የእኛ ከንቲባ!» በማለት በይበልጥ አንቆ ያዘው::
መሴይ ማንደላይን አንገቱን ለማስለቀቅ አልሞከረም፡፡ ግን «ዣቬር» ሲል ተናገረ::
ዣቬር ጣልቃ በመግባት አቋረጠው:: ክቡር የፖሊስ አዛዥ ብለህ ጥራኝ» አለው::
«ክቡር» አለ ዣን ቫልዣ ፧ ብቻችንን ብንሆን አንድ የምጠይቅህ ነገር
ነበረኝ::
«ጮክ በል፣ ድምፅህን ከፍ ኣድርገህ ተናገር:: ሰዎች እኔን ሲያናግሩ ጮክ እያሉ ነው የሚያነጋግሩኝ» አለ ዣቬር፡፡
ድምፁን ዝቅ አድርጎ ዣን ቫልዣ ንግግሩን ቀጠለ::
«አንተን በግል የምለምንህ ጉዳይ አለኝ፡፡››
‹‹ጮክ ብለህ ተናገር ብዬህ እኮ ነበር፡፡»
«ግን የምነግርህ ነገር እኔና አንተ እንጂ ሌላ ሰው መስማት ስለሌለበት ነው::
“ጉዳዩ መሰለህ፤ በአንተ ጉዳይ እኔን ምን አስጨነቀኝ፣ አልሰማም::
ዣን ቫልዣ ጠጋ ብሎ በችኮላ አሁንም ድምፁን ዝቅ እድርጎ
የሚከተለውን ተናገረ::
« ሦስት ቀን ብቻ ስጠኝ! የዚህች የተከፋች ሴት ልጅ ሄጄ ላምጣላት::የሚያስፈልገውን ወጪ በሙሉ እኔ እከፍላለሁ:: ከፈለግክ አብረን ልንሄድ እንችላለን፡፡
«በእኔ ላይ ነው የምታሾፈው» አለ ዣቬር፡፡ «እስከዚህ ሞኝ
አትመሰለኝም ነበር:: ሦስት ቀን ስጠኝና የዚህችን ሴት ልጅ ላምጣ' ትለኛለህ:: በጣም ታስቃለህ፡፡»
የፋንቲን ሰውነት ተንቀጠቀጠ፡፡
«ልጄን» ስትል ጮኸች፡፡ «ልጄ ዘንድ ሊሄዱ ነዋ! ወይኔ ልጄ፧
አልመጣችም ማለት ነዋ! ሲስተር ይንገሩኝ፤ ልጄ የት ናት? መሴይ
ማንደላይን፤ ክቡር ከንቲባ ልጄን እፈልጋታለሁ!»
ዣቬር ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት መሬቱን በጫማው ረገጠው::
#ገረገራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
“ምንድነዉ እመ?”
እየቆየ ፍርሐት እየለቀቀብኝ፣ ላብ እያጠመቀኝ መጣ፡ ቢያንስ ቢያንስ እንዴት ድምፅዋን እንኳን አልሰማሁትም? ለምን አላለቀሰችም? “ኧረ ልጄስ? ልጄ አታመጡልኝም?” አልሁኝ ከአሁን አሁን ቱናትን አምጥተዉ ያስታቅፉኛል ብዬ ብጠብቅ ዝም ስላሉኝ፡ አጭር ጊዜ በፈጀ
ቀዶ ሕክምና ቢሆንም የወለድሁት፣ የእናት ወጉ ደርሶኝ ገና ጡቴን ለልጄ አላጠባኋትም ጡት ማጥባት ቀርቶ ለዓይኔ እንኳን አላሳዩኝም፡
“አይ፣ ለትንሽ ጊዜማ ማሞቂያ ክፍል አትቆይም ብለሽ ነዉ? እንግዲህ ዶክተርሽ ያለችን እንደዚያ ነዉ” አለች እመዋ፣ ከእሸቴና ባልቻ ጋር የያዘችዉን ሞቅ ያለ ጨዋታ አቋርጣ ትኩረት እየሰጠችኝ፡
“እኮ ባይሆን አሳዩኛ። ላያት እፈልጋለሁ”
“ቆይ ትንሽ ተብለሽ እኮ ነዉ: አንቺም ትንሽ አረፍ በይ እስኪ ፊት”
“እመዋ፤ ወይ ወደ ልጄ ዉሰጅኝ ወይ ደሞ ልጄን አምጭልኝ” አልሁኝ፣ ከአልጋዬ ላይ ለመነሳት እየተገለገልሁ አቅም አጣሁ እንጂ ማንም አይመልሰኝም ነበር ለምንም ነገር እንዲህ ሆኜ አላዉቅም ለካ እንዲህ ነዉ የሚያደርገዉ? አሁን በአሁን እናት ሆኜ እርፍ! የእናት ሆድ ኖሮኝ
ቁጭ! ጭራሹን ያላየኋት ልጄ በዓይን በዓይኔ ዞረች᎓᎓ ናፈቀችኝ፡ ራበችኝ፡ ደግሞ ልቤ እንዴት ነዉ የሚደልቀዉ? ልጄን እንጂ የፍርድ ቤት ዳኛ አይደል የምተያየዉ፡
የናፍቆቱስ እሺ ይገባኛል፤ ፍርሃቱን ግን ምን አመጣዉ?
የልቤ መንቀጥቀጥ ቆዳዬ ላይ እስከሚታወቅ ድረስ በጣም ፈርቻለሁ ጭንቅላቷን ማየት ነዉ ፤ያስፈራኝ: ትልቅነቱ ምን አህሎ ይሆን? ራሷስ ምን ታህል ይሆን? ኹለት ኪሎ እንኳን መሙላቷን እንጃ አተነፋፈሷ ልክ ነዉ? በቅድመ ወሊድ እንደ ተፈራዉ፣ የጀርባዋ ነርቭ ክፍተት ፈጥሮ ይሆን? ቢያንስ እግሮቿን ማንቀሳቀስ ትችልም እንደሆነ
እኮ ገና የነገረኝ የለም: ዓይኖቿም በትክክል ማየታቸዉን አላወቅሁም
ወይስ እግዚአብሔር ተአምር ሠራ? ባልቻ እና እመዋ እንደ ተማመበት ድንቅ ሥራዉን አሳይቷቸዉ ይሆን? በተአምሩ የሰዉ መልክ፣ የሰዉ ጤና፣ የሰዉ ትንፋሽ ሰጥቷትስ ቢሆን! እሱንስ ቢሆን ማን ነገረኝ?
እግዚአብሔር እኮ ሥራዉ የሚታወቀዉ አንድም በጨቅላዎች ነዉ ይባላል፡፡ ከማሕጸን እንደ ወጡ ገና የጡትን ቦታ እና ጥቅም አጥተዉት
አያዉቁም: ልጄንስ ጡት አያምራት ይሆን? ካላየኋትማ መሞቴ ነዉ፡
እንደገና ፈራኋት ፡ እንደገና ናፈቅኋት።
“አንቺ ግን አየሻት ወይ እመ?” አልኋት፣ እጆቼን ከጡቶቼ ላይ ሳላነሳ።
“ማንን፣ ቱናትን?”
“አሃ፤ ስምም አዉጥታችሁላታላ?” አለ ባልቻ፣ ከእመዋ አፍ ተቃምቶ።
“ቱናት ብያታለሁ በበኩሌ” አለች፣ እመዋ:
“እመዋ” ስል ጠራኋት ቆጣ ብዬ፣ የባልቻ አጠያየቅ ወሬ ለመለወጥ
መሆኑ ስለ ገባኝ፡
“ዉብዬዋ” አለችኝ፣ የእናት እጇን ጭምር እየሰጠችኝ ይኼዋ እንዴት
እንደምታቆለማምጠኝ! ቁልምጫዋንስ ማቆላመጥ ታዉቅበት የለ? እሷ እናትነቷን እንዲህ ባጠጣችኝ ቁጥር፣ የእኔም ጉጉት ሰማይ ይደርሳል
እሷ ለእኔ እንደምትሆነዉ፣ እኔም ለልጄ ለመሆን ቋምጫለሁ
“እመዋ”
“እመት ዓለሜዋ”
“ስሞትልሽ! ስሞትልሽ ልጄን አምጭልኝ'
“ኧረ ቀስ! ምነዉ ልጄ? ወዲያዉስ የሐኪምሽ ወዳጅነት ላንቺ መስሎኝ! እንዲህ ሆነሽ ትወስድሽ ሆይ ወይ ደግሞ ቱናትን እንዲያ እዳለች ታመጣልሽ እንደሆነ፤ ሐኪምሽን ራስሽ የማትጠይቂያት”
"እኮ ጥሪልኛ እመዋ ዶክተሯን ጥሪልኝ እሺ”
እንደማልለቃቸዉ ሲያዉቁ ዶክተሯን ማስፈለግ ጀመሩ፡ ነገር ግን ሌላ ተረኛ ነፍሰ ጡር ለማዋለድ፣ ወደ ማዋለጃ ክፍል ቅርብ ጊዜ እንደ ገባች ከነርሶቹ መስማታቸዉን ነገሩኝ፡
አላመንኋቸዉም በይበልጥ
እየፈራሁላት፣ በይበልጥ እየተጠራጠርኋቸዉ መጣሁ ቅጽበት በቆየሁ ቁጥር ክፉ ክፉዉን ለሚያሳስበኝ መንፈስ መረታት ያዝሁ፡ ጭራሽ በሕይወት ባትኖር ይሆናል እንጂ፣ ቢያንስ እንዴት ድምፁዋን እንኳን
አያሰሙኝም?
“አአአ..አንድ ሐሳብ መመመመ..መጣልኝ” ሲል ሰማሁት እሸቴን፣ እስከ
አሁን ዓይኖቹን ከማንከራተት በቀር ትንፍሽ ሳይል ቆይቶ፡ “ዉዉዉ..
ዉቤ? ”
“እየሰማሁህ ነዉ”
ሐሳቡን አንድ ብሎ ሊነግረኝ ሲጀምር ገና፣ ልታዋልድ ኦፕራሲዮን ክፍል ገብታለች የተባለችዋ ዶክተር የክፍሉን በር ከፍታ ገባች፡
“ኦንኳን ማርያም ማረችሽ” አለችኝ፡
“ማርያም ታኑርሽ” አለች እመዋ ቀድማኝ ወዲያዉም ከጎኔ ቁጭ
ካለችበት የአልጋዉ ጫፍ ብድግ ብላ፡ ዶክተር ሸዊት ያ ብዙም
የማይለያትን ፈገግታዋን
ሳትቀንስ ሁሉንም እያቀፈች ሰላምታ ከተለዋወጠች በኋላ፣ እኔንም ጎንብስ ብላ ሳመችኝ፡፡ ግንባሬን አንገቴን እና እጆቼን እየደባበሰችኝ ሳለ፣ ለምን ልጄን እንደማያመጡልኝ ልጠይቃት ስል ቀልቧን ወደ እመዋ አደረገችብኝ፡፡
“እመዋ? እንኳን ደስ አለዎ”
“በአምላክሽ!”
“መቼስ ረስተዉኝ አይሆንም፤ ረሱኝ እንዴ ? "
“ተይ እንጂ! ምን ብረሳ ብረሳ፣ አንቺን እረሳ ብለሽኝ ነዉ? ምነው
አንድዜ እንኳ ከዉብዬ ጋ ለክረምቱ ይሁን ለገናዉ ዕረፍት
መጥታችሁ አብረንም አልሰነበትን?”
“አልረሱኝማ”
“ አንቺን? እንዲያዉ ያቺን ጨዋታሽ የምረሳልሽ መስሎሻል?”
“የቷን?” አለች፣ ለመፍካት ችኩል የሆኑ ጥርሶቿን እየገለጠች
“ምነዉ እንኳን አንድዜ፣ የሩስያ ምንቴስ ነዉ ያልሽኝ ሰዉ በዉብርስቴ ደም ግባት የሆነዉን ሁሉ አጫዉተሽኝ?”
“ስለ እሱ ጉድ ነግሬሽ ነበር ወይ እመዋ?”
“እህሳ”
“ለእኛም ንገሪን እንጂ ዶክተር” አለ ባልቻ፣ ያለ ወትሮዉ ለወሬ ሰፍ ብሎ፡ የእሸቴም ጆሮ ከምኔዉ ቀጥ እንዳለ! የእሸቴ እና የባልቻስ ይሁን እሺ፣ እመዋ እንኳን እንደ አዲስ ለመስማት በዓይኖቿ ደጅ ስትጠናት ሳይ እኔም የልጄ ናፍቆት በረድ አለልኝ፡፡
“ጉዷ ያልቅ መስሏችኋል?” ብላ ጀመረች፡ “ይቺ ጉደኛ! የተመረቅን
ሰሞን ነዉ ነገሩ። ቀድሞዉንም ቢሆን በዉጤት እንደ ምንም እቀራረባት እንደሆነ እንጂ ደርሼባት አላውቅም:: በተለይ የመመረቂያ ጥናቷን ያዩላት ሰዎች ሁሉ እዴት ይደነቁባት እንደነበር አትጠይቁኝ። እና እንደ አጋጣሚ፣ በዚያ ሰሞን የሩስያ አምባሳደር ከሀገራቸዉ የመጡ በጎ ፈቃደኛ
ሀኪሞችን እየመሩ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ መጥተዋል። ጠሪዉ ደግሞ የጎንደር ዩኒቨርስቲ ነዉ: የዚያን ዕለት ታዲያ፣ የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዜዳንት ራሱ ስልክ ደዉሎላት ኹለት ሁነኛ ሰዎች እንድትመርጥ እና በጎ ፈቃደኛ ሩስያዊ ሀኪሞችን እንድታግዝ ያዝዟታል”
“ማንን?”
“ይቺን ነዋ፤ ዉብርስትን''
“እሺ”
"እሷ ደግሞ እኔን እና አንድ ሌላ ሐኪም ስትጠይቀን፣ እናግዛለን ብለን ሳይሆን እንጠቀማለን ብለን ወደ ተባሉት በጎ አድራጊዎች በጠዋት †ነስተን ተከተልናት።
በዚያች አንድ ቀን ታዲያ፣ ሩስያዉያኑ ያልደረሱበት የጎንደር ዙሪያ ጤና ጣቢያ የለም። እኛም አብረናቸዉ እየዞርን እነሱ ለጤና ጣቢያዎቹ ያመጡልን መድኃኒት ስናድል እና ለጥቂት አበሻ ሕመምተኞች ደግሞ መጠነኛ ሕክምና ሲሰጡ ስናይ ዋልን
ማታዉኑ፣ ዩኒቨርስቲዉ እንግዶቹን እራት ካልጋበዝሁ አለ። አምባሳደሩ ግን አመሻሹ ላይ ወደ አዲስ አበባ መመለስ ቢሆንም ዕቅዳቸዉ፣ ከስንት መለመን በኋላ የበረራ ሰዓታቸዉ እንዲዘገይ ተስማምተዉ በግብዣዉ ላይ
ተገኙ። እኛም እንደ እንግዶች በክብር ተጠርተን፣ መጥሪያዉ ላይ በተጠቀሰዉ ባለ አራት ኮከብ ሆቴል ተገኝተናል። የከተማዉ ከንቲባ፣ የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዜዳንት፣ምክትሎቻቸዉ እና ዘመዶቻቸዉ ጭምር
መጥተዉ ሳይሆን አይቀርም፣ ያን የሚያህል አዳራሽ ጢም ብሏል።
የጎንደር መታወቂያ የሚባሉ አዝማሪዎችም መድረኩን ሞልተዉታል።ብርቆዎች፣ ጨዋታዎች፣ ሳቆች ድብልቅልቅ አድር ገዉታል”
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በታደለ_አያሌው
“ምንድነዉ እመ?”
እየቆየ ፍርሐት እየለቀቀብኝ፣ ላብ እያጠመቀኝ መጣ፡ ቢያንስ ቢያንስ እንዴት ድምፅዋን እንኳን አልሰማሁትም? ለምን አላለቀሰችም? “ኧረ ልጄስ? ልጄ አታመጡልኝም?” አልሁኝ ከአሁን አሁን ቱናትን አምጥተዉ ያስታቅፉኛል ብዬ ብጠብቅ ዝም ስላሉኝ፡ አጭር ጊዜ በፈጀ
ቀዶ ሕክምና ቢሆንም የወለድሁት፣ የእናት ወጉ ደርሶኝ ገና ጡቴን ለልጄ አላጠባኋትም ጡት ማጥባት ቀርቶ ለዓይኔ እንኳን አላሳዩኝም፡
“አይ፣ ለትንሽ ጊዜማ ማሞቂያ ክፍል አትቆይም ብለሽ ነዉ? እንግዲህ ዶክተርሽ ያለችን እንደዚያ ነዉ” አለች እመዋ፣ ከእሸቴና ባልቻ ጋር የያዘችዉን ሞቅ ያለ ጨዋታ አቋርጣ ትኩረት እየሰጠችኝ፡
“እኮ ባይሆን አሳዩኛ። ላያት እፈልጋለሁ”
“ቆይ ትንሽ ተብለሽ እኮ ነዉ: አንቺም ትንሽ አረፍ በይ እስኪ ፊት”
“እመዋ፤ ወይ ወደ ልጄ ዉሰጅኝ ወይ ደሞ ልጄን አምጭልኝ” አልሁኝ፣ ከአልጋዬ ላይ ለመነሳት እየተገለገልሁ አቅም አጣሁ እንጂ ማንም አይመልሰኝም ነበር ለምንም ነገር እንዲህ ሆኜ አላዉቅም ለካ እንዲህ ነዉ የሚያደርገዉ? አሁን በአሁን እናት ሆኜ እርፍ! የእናት ሆድ ኖሮኝ
ቁጭ! ጭራሹን ያላየኋት ልጄ በዓይን በዓይኔ ዞረች᎓᎓ ናፈቀችኝ፡ ራበችኝ፡ ደግሞ ልቤ እንዴት ነዉ የሚደልቀዉ? ልጄን እንጂ የፍርድ ቤት ዳኛ አይደል የምተያየዉ፡
የናፍቆቱስ እሺ ይገባኛል፤ ፍርሃቱን ግን ምን አመጣዉ?
የልቤ መንቀጥቀጥ ቆዳዬ ላይ እስከሚታወቅ ድረስ በጣም ፈርቻለሁ ጭንቅላቷን ማየት ነዉ ፤ያስፈራኝ: ትልቅነቱ ምን አህሎ ይሆን? ራሷስ ምን ታህል ይሆን? ኹለት ኪሎ እንኳን መሙላቷን እንጃ አተነፋፈሷ ልክ ነዉ? በቅድመ ወሊድ እንደ ተፈራዉ፣ የጀርባዋ ነርቭ ክፍተት ፈጥሮ ይሆን? ቢያንስ እግሮቿን ማንቀሳቀስ ትችልም እንደሆነ
እኮ ገና የነገረኝ የለም: ዓይኖቿም በትክክል ማየታቸዉን አላወቅሁም
ወይስ እግዚአብሔር ተአምር ሠራ? ባልቻ እና እመዋ እንደ ተማመበት ድንቅ ሥራዉን አሳይቷቸዉ ይሆን? በተአምሩ የሰዉ መልክ፣ የሰዉ ጤና፣ የሰዉ ትንፋሽ ሰጥቷትስ ቢሆን! እሱንስ ቢሆን ማን ነገረኝ?
እግዚአብሔር እኮ ሥራዉ የሚታወቀዉ አንድም በጨቅላዎች ነዉ ይባላል፡፡ ከማሕጸን እንደ ወጡ ገና የጡትን ቦታ እና ጥቅም አጥተዉት
አያዉቁም: ልጄንስ ጡት አያምራት ይሆን? ካላየኋትማ መሞቴ ነዉ፡
እንደገና ፈራኋት ፡ እንደገና ናፈቅኋት።
“አንቺ ግን አየሻት ወይ እመ?” አልኋት፣ እጆቼን ከጡቶቼ ላይ ሳላነሳ።
“ማንን፣ ቱናትን?”
“አሃ፤ ስምም አዉጥታችሁላታላ?” አለ ባልቻ፣ ከእመዋ አፍ ተቃምቶ።
“ቱናት ብያታለሁ በበኩሌ” አለች፣ እመዋ:
“እመዋ” ስል ጠራኋት ቆጣ ብዬ፣ የባልቻ አጠያየቅ ወሬ ለመለወጥ
መሆኑ ስለ ገባኝ፡
“ዉብዬዋ” አለችኝ፣ የእናት እጇን ጭምር እየሰጠችኝ ይኼዋ እንዴት
እንደምታቆለማምጠኝ! ቁልምጫዋንስ ማቆላመጥ ታዉቅበት የለ? እሷ እናትነቷን እንዲህ ባጠጣችኝ ቁጥር፣ የእኔም ጉጉት ሰማይ ይደርሳል
እሷ ለእኔ እንደምትሆነዉ፣ እኔም ለልጄ ለመሆን ቋምጫለሁ
“እመዋ”
“እመት ዓለሜዋ”
“ስሞትልሽ! ስሞትልሽ ልጄን አምጭልኝ'
“ኧረ ቀስ! ምነዉ ልጄ? ወዲያዉስ የሐኪምሽ ወዳጅነት ላንቺ መስሎኝ! እንዲህ ሆነሽ ትወስድሽ ሆይ ወይ ደግሞ ቱናትን እንዲያ እዳለች ታመጣልሽ እንደሆነ፤ ሐኪምሽን ራስሽ የማትጠይቂያት”
"እኮ ጥሪልኛ እመዋ ዶክተሯን ጥሪልኝ እሺ”
እንደማልለቃቸዉ ሲያዉቁ ዶክተሯን ማስፈለግ ጀመሩ፡ ነገር ግን ሌላ ተረኛ ነፍሰ ጡር ለማዋለድ፣ ወደ ማዋለጃ ክፍል ቅርብ ጊዜ እንደ ገባች ከነርሶቹ መስማታቸዉን ነገሩኝ፡
አላመንኋቸዉም በይበልጥ
እየፈራሁላት፣ በይበልጥ እየተጠራጠርኋቸዉ መጣሁ ቅጽበት በቆየሁ ቁጥር ክፉ ክፉዉን ለሚያሳስበኝ መንፈስ መረታት ያዝሁ፡ ጭራሽ በሕይወት ባትኖር ይሆናል እንጂ፣ ቢያንስ እንዴት ድምፁዋን እንኳን
አያሰሙኝም?
“አአአ..አንድ ሐሳብ መመመመ..መጣልኝ” ሲል ሰማሁት እሸቴን፣ እስከ
አሁን ዓይኖቹን ከማንከራተት በቀር ትንፍሽ ሳይል ቆይቶ፡ “ዉዉዉ..
ዉቤ? ”
“እየሰማሁህ ነዉ”
ሐሳቡን አንድ ብሎ ሊነግረኝ ሲጀምር ገና፣ ልታዋልድ ኦፕራሲዮን ክፍል ገብታለች የተባለችዋ ዶክተር የክፍሉን በር ከፍታ ገባች፡
“ኦንኳን ማርያም ማረችሽ” አለችኝ፡
“ማርያም ታኑርሽ” አለች እመዋ ቀድማኝ ወዲያዉም ከጎኔ ቁጭ
ካለችበት የአልጋዉ ጫፍ ብድግ ብላ፡ ዶክተር ሸዊት ያ ብዙም
የማይለያትን ፈገግታዋን
ሳትቀንስ ሁሉንም እያቀፈች ሰላምታ ከተለዋወጠች በኋላ፣ እኔንም ጎንብስ ብላ ሳመችኝ፡፡ ግንባሬን አንገቴን እና እጆቼን እየደባበሰችኝ ሳለ፣ ለምን ልጄን እንደማያመጡልኝ ልጠይቃት ስል ቀልቧን ወደ እመዋ አደረገችብኝ፡፡
“እመዋ? እንኳን ደስ አለዎ”
“በአምላክሽ!”
“መቼስ ረስተዉኝ አይሆንም፤ ረሱኝ እንዴ ? "
“ተይ እንጂ! ምን ብረሳ ብረሳ፣ አንቺን እረሳ ብለሽኝ ነዉ? ምነው
አንድዜ እንኳ ከዉብዬ ጋ ለክረምቱ ይሁን ለገናዉ ዕረፍት
መጥታችሁ አብረንም አልሰነበትን?”
“አልረሱኝማ”
“ አንቺን? እንዲያዉ ያቺን ጨዋታሽ የምረሳልሽ መስሎሻል?”
“የቷን?” አለች፣ ለመፍካት ችኩል የሆኑ ጥርሶቿን እየገለጠች
“ምነዉ እንኳን አንድዜ፣ የሩስያ ምንቴስ ነዉ ያልሽኝ ሰዉ በዉብርስቴ ደም ግባት የሆነዉን ሁሉ አጫዉተሽኝ?”
“ስለ እሱ ጉድ ነግሬሽ ነበር ወይ እመዋ?”
“እህሳ”
“ለእኛም ንገሪን እንጂ ዶክተር” አለ ባልቻ፣ ያለ ወትሮዉ ለወሬ ሰፍ ብሎ፡ የእሸቴም ጆሮ ከምኔዉ ቀጥ እንዳለ! የእሸቴ እና የባልቻስ ይሁን እሺ፣ እመዋ እንኳን እንደ አዲስ ለመስማት በዓይኖቿ ደጅ ስትጠናት ሳይ እኔም የልጄ ናፍቆት በረድ አለልኝ፡፡
“ጉዷ ያልቅ መስሏችኋል?” ብላ ጀመረች፡ “ይቺ ጉደኛ! የተመረቅን
ሰሞን ነዉ ነገሩ። ቀድሞዉንም ቢሆን በዉጤት እንደ ምንም እቀራረባት እንደሆነ እንጂ ደርሼባት አላውቅም:: በተለይ የመመረቂያ ጥናቷን ያዩላት ሰዎች ሁሉ እዴት ይደነቁባት እንደነበር አትጠይቁኝ። እና እንደ አጋጣሚ፣ በዚያ ሰሞን የሩስያ አምባሳደር ከሀገራቸዉ የመጡ በጎ ፈቃደኛ
ሀኪሞችን እየመሩ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ መጥተዋል። ጠሪዉ ደግሞ የጎንደር ዩኒቨርስቲ ነዉ: የዚያን ዕለት ታዲያ፣ የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዜዳንት ራሱ ስልክ ደዉሎላት ኹለት ሁነኛ ሰዎች እንድትመርጥ እና በጎ ፈቃደኛ ሩስያዊ ሀኪሞችን እንድታግዝ ያዝዟታል”
“ማንን?”
“ይቺን ነዋ፤ ዉብርስትን''
“እሺ”
"እሷ ደግሞ እኔን እና አንድ ሌላ ሐኪም ስትጠይቀን፣ እናግዛለን ብለን ሳይሆን እንጠቀማለን ብለን ወደ ተባሉት በጎ አድራጊዎች በጠዋት †ነስተን ተከተልናት።
በዚያች አንድ ቀን ታዲያ፣ ሩስያዉያኑ ያልደረሱበት የጎንደር ዙሪያ ጤና ጣቢያ የለም። እኛም አብረናቸዉ እየዞርን እነሱ ለጤና ጣቢያዎቹ ያመጡልን መድኃኒት ስናድል እና ለጥቂት አበሻ ሕመምተኞች ደግሞ መጠነኛ ሕክምና ሲሰጡ ስናይ ዋልን
ማታዉኑ፣ ዩኒቨርስቲዉ እንግዶቹን እራት ካልጋበዝሁ አለ። አምባሳደሩ ግን አመሻሹ ላይ ወደ አዲስ አበባ መመለስ ቢሆንም ዕቅዳቸዉ፣ ከስንት መለመን በኋላ የበረራ ሰዓታቸዉ እንዲዘገይ ተስማምተዉ በግብዣዉ ላይ
ተገኙ። እኛም እንደ እንግዶች በክብር ተጠርተን፣ መጥሪያዉ ላይ በተጠቀሰዉ ባለ አራት ኮከብ ሆቴል ተገኝተናል። የከተማዉ ከንቲባ፣ የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዜዳንት፣ምክትሎቻቸዉ እና ዘመዶቻቸዉ ጭምር
መጥተዉ ሳይሆን አይቀርም፣ ያን የሚያህል አዳራሽ ጢም ብሏል።
የጎንደር መታወቂያ የሚባሉ አዝማሪዎችም መድረኩን ሞልተዉታል።ብርቆዎች፣ ጨዋታዎች፣ ሳቆች ድብልቅልቅ አድር ገዉታል”
#ሳቤላ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
....ቀና አለችና እስከ መቸም ከልቡ በማይጠፋ አመለካከት አየችው " እሱም የተስፋ መቁረጥ አስተያየት መሆኑ ቶሎ ገባው "
“ አይደለም ” አለችው ራሷን ነቅንቃ ። “የሥቃይ ቤት ነው እኔም ከእንግዲህ ከዚህ ቤት መኖር አልችልም " ወዴት አባቴ እንደምሔድ ዛሬ ሌሊት ሳስብ
አንዳችም ብልሃት ሳላገኝ ተጎልቸ አደርኩ " እኔ በዚህ ሰፊ ዓለም አንድም ሁነኛ ሰው የለኝም "
ከልጆች ፌት ምስጢር መጫወት ተገቢ አይደለም ከሚገምቱት በላይ መስማትና ማስተዋል እንደሚችሉ ማወቁ ተገቢ ነው ትንንሽ ጋኖች ትልልቅ ጆሮዎች
አሏቸው የሚባለው አነጋገር የሚያስገርም ሐቅ ነው ሎርድ ቬን አንገቱን ቀና አድርጎ ሚስተር ካርላይልን ሽቅብ ይመለከተው ጀመር "
“ ሳቤላ “ ኮ ከኛ ቤት እወጣለሁ ብላ ዛሬ ጧት ነገረችኝ " ለምን እንደሆነ ልንገርዎት ? ትናንት ማታ እማማ ተናድዳ ስለ መታቻት ነው "
“ ዝም በል ዊልያም ” ብላ አቋረጠችው ሳቤላ „ “ ሁለት ጊዜ በጥፌ መታቻት ጉንጮ ላይ ” አለና ልጁ ነገሩን በመቀጠል “ሳቤላም አለቀሰች እኔም ጮህኩ በዚህ ጊዜ እማማ እኔንም አጮለችኝ " ልጆች ለመመታት ነዉ የተፈጠሩት ትላለች ሞግዜቴ። ሻይ ስንጠጣ ማርቨል መጥታ ለሞግዚቴ ነገረቻት እማማ ሳቤላን የምትመታት እኮ ሳቤላ በመልክ ስለምትበልጣት ...>>
ሳቤላ ፡ አፉን ይዛ አቋረጠችውና አንዲት ሠራተኛ ጠርታ ወደ ልጆች ክፍል አስወሰደችው : የሚስተር ካርላይል ዐይኖች በንዴትና በኅዘን ብርዝ አሎ „ “ እውነት ነው ? ” አላት ፊቷን ወደሱ ምልስ ስታደርግ “ እውነትም ሁነኛ ሰው ያስፈልግሻል።
ዕድሌ የጣለብኝን ዕጣ መቀበል አለብኝ ' ሲቀር ሲውል ሎርድ ማውንት እስቨርን እስኪመለስ ድረስ ”
“ ከዚያ በኋላስ ምን ትሆኛለሽ ? ''
ከዚያ በኋላ የምሆነውን ምንም አላውቅም ” አለችው ልማደኛው እንባዋ ልትቈጣጠረው ከማትችለው ፍጥነት በላይ እየገነፈለ „ “ እሱ ለኔ የሚሰጠኝ ሌላ ቤት የለውም ። እኔ ደግሞ ከወይዘሮ ማውንት እስቨርን ጋር አብሬ መኖር አልችልም "
መንፈሴን ድቅቅ አድርጋ እንደ ስበረችው ሁሉ አሁንም ልቤን ታፈሰዋለች » እኔ በሷ ይህን ያሀል መበደል የሚገባኝ ስው አልነበርኩም ... ሚስተር ካርላይል
በርግጥ አልነበርሽም ” አላት ሚስተር ካርላይል “ አሁን ምን ላድርግልሽ እችላለሁ ? ''
“ አሁን አንተም ሆንክ ሌላ ምንም ሊያደርግልኝ አይችልም : ”
“ አንቺን መርዳት የምችልበት መንገድ ባገኝ በጣም ደስ ይለኝ ነበር " መቸም ኢስትሊንም ላንቺ የደስታ ቤት አልነበረም ነገር ግን ከለቀቅሺው ወዲህ የባሰ ተጐሳቁለሻል
የደስታ ቤት አልነበረም አልከኝ ? ” አለችው የኢስትሊን የኑሮ ትዝታ ድቅን እያለባት “ ኧረ እሱስ ነበረ እንግዲህም እንደሱ ደስ የሚል ኑሮ የማገኝ አይመስለኝም ሚስርተር ካርላይል ኢስትሊንን አቃለህ አትንገረኝ " ምነው አሁን
እነዚያ ያሳለፍኩዋቸው የመከራ ወሮች ወደ ሕልም በተለወጡና አባቴን በሕይወቱ አግኝቸው ኢስትሊን ውስጥ እንደ ዱሮአችን በሰላም ስኖር ከእንቅልፌ በነቃሁ . .
“ ወደ ኢስትሊን የምትመለሽበት አንድ መንገድ ብቻ አለ ” አላት መንፈሱ ጭንቅ ጭንቅ እያለው ልቡ በጣም እየመታ እጂዋን ያዝ አድርጎ ምናልባትም ሳይታወቀው ሊሆን ይችላል · ጣቶቹ ከጣቶቿ ጋር እየተጫወቱ " ንግግሬ የሚያስከፋሽ ከሆነ መልሽኝ : በጥፋቴም ይቅርታ አድርጊልኝ "የኢስትሊን እመቤት ሆነሽ
እንድትመለሽበት ብጠይቅሽ ድፍሬት ይሆንብኛል ? ”
ምን ለማለት እንደ ፈለገ ፍጹም አልገባትም „ “እመቤት ሁኜ ወደ ኢስትሊን መመለስ ? ” አለችው ድንግጥ ብላ "
“ አዎን ' የኢስትሊን እመቤት የኔ ባለቤት ሆነሽ " ብሎ መላሰላት
አሁን ገባት መገረምም መደንገጥም †ነባበሩባት " በርግጥ ሚስተር ካርላይል
ብዙ ውለታ የዋለላት ከደግንቱ እንከን ያላገኘችበት ሰው ስለነበር ትወደው ነበር ሚስቱ የመሆን ጉዳይግን እሱ አፍ አውጥቶ እስከ ጠየቀበት ሰዓትድረስ አሰባው
አታውቅም ደነገጠችም ለዚሁ ነበር እጅዋንም ከእጁ አስለቅቃ ሊሆን እንደማይችል ልትነግረው ቃጣትና እጅዋን ሳብ ስታደርግ እሱ ደግሞ ጠበቅ አደረጋት።
የመናገር ፈራ ተባው ለቀቀው " ጠቅላላ ስለሷ ያለውን ስሜት የትዳሩን ዓላማና የፍቅሩን ነገር በማይስቱና ልብን በሚወጉ የቃላት ቀስት ነደፋት ልብን በሚነካ ንግግር ሐሳቡን በሙሉ በምታውቀው ሐቀኝነቱ ግልጽልጽ አድርጎ አጫታት ሁለቱ በዚህ ሁኔታ እንዳሉ ወይዘሮ ማውንት እስቨርን ገባች ደነገጠችና ምንም ሳትናገር በሐሳቧ ብቻ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ የምትጠብቅ
ይመስል ቀጥ ብላ ቆመች።
ሚስተር ካርላይል ሳቤላን ያዳነ መሰለውና ራሱን ለማስተዋወቅ ወደሷ ቀረብ ሲል ሳቤላ ደግሞ ተረጋጋችና “ ወይዘሮ ማውንት እስቨርን ” ብላ አስተዋወቀች ,
ሎርድ ማውንት እስቨርን ባለመኖራቸው በጣም አዝናለሁ " እሳቸው ያውቁኝ ነበር እኔ ሚስተር ካርላይል እባላለሁ ” አላት "
“እኔም ስለአንተ ሰምቻለሁ " አለችው ሸጋ መልኩን እየቃኘችና አክብሮቴን ለማትወዳት ሴት ሲሰጥ በማየቷ ቅር እያላት “ከወይዘሮ ሳቤላ ቬን ጋር ይኸን ያህል የቀረበ ወዳጅነት እንዳላችሁ ግን አልሰማሁም " ”
“ እስካሁን እንኩዋን ለእርስዎ የመሰለዎትን ያህል የጠና ወዳጅነት አልነበረንም” አላት ወንበር ጠጋ ካዪረገላት በኋላ ለራሱም ሌላ እያስተካከለ „ “ አሁን ግን ወዳጅነታችንን የጠና ለማድረግ ሚስቴ እንድትሆን እየለመንኳት ነበር '
እመቤቲቱ ከዚያች ከምትጠላት ልጅ የምትላቀቅበት ፍንጭ በማግኘቷ የከፋው ፊቷ የደስታ ብርሃን ፈነጠቀበት " ሚስተር ካርላይልን እንደ ትልቅ ባለውለታዋ
አድርጋ አየችው ።
“ግድ የለሹ አባቷ ያለምንም አለኝታ ጥለዋት እንደሞቱ • አንተም ታውቃለህ ስለዚህ እንደዚህ ያለ ከፍተኛ የጋብቻ ጥያቄ ሲቀርብላት ሳቤላ በደስታ መቀበል አለባት " ደግሞም እንደ ሰማሁት ኢስትሊን በጣም የሚያምር ቦታ ነው ይባላል
አለችውና ፊቷን ወደ ሳቤላ መልሳ “ ለመሆኑ የሷ መልስ ምንድነው? ” ብላ ጠየቀችው።
ኅቤላ ለሷ በቀጥታ መልስ እንደ መስጠት ራሷን ዝቅ እንደ ማድረግ ቆጠረችውና ሚስተር ካርላይልን 'እንዳስብበት ጥቂት ሰዓት ልትሰጠኝ ትችላለህ ? '' አለችው "
“ በነገሩ በደንብ ብታስቢበት ለኔም በጣም ደስ ይለኛል " ስለዚህ ከሰዓት በኋላ እመለሳለሁ ” ብሏት ሔደ ።
ሚስተር ካርይል ከወይዘሮ ማውንት እስቨርን ጋር ሲነጋገር ሳቤላ ከክፍሏ ግብታ ብቻዋን በጣም ግራ የሚያጋባ ሙግት ጀመረች " ሳቤላ ከልጅ እምብዛም
አትሻልም ነበር አስተሳሰቧና ክርክሯ ሁሉ እንዶ ልጅ ላይ ላዩን እንጂ ጥልቀትና ብስለት አልነበረውም " ሚስተር ካርላይል የተራ ቤተሰብ ልጅ መሆኑንና እንደሷ ከትልቅ ሰው ባለወለዱ አቻዋ ያለመሆኑን ነገር አላሰበችውም " ኢስትሊን ለዘለቄታ መኖሪያነት ጥሩ ቦታ ነበር " በመጠን በውበትና በጠቃሚነትም ረገድ
አሁን ከምትኖርበት ከካስል ማርሊንግ በጣም የላቀ ነበር " ነገር ግን ኢስትሊንን የሚስተር ካርላይል ሚስት ሆና ስትገባበት የሎርድ ማውንት እስቨርን ልጅ ሆና እንደ ኖረችበት እንደማይሆንላት አላሰበችውም " ተወልዳ ካደገችበት ድምቀት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
....ቀና አለችና እስከ መቸም ከልቡ በማይጠፋ አመለካከት አየችው " እሱም የተስፋ መቁረጥ አስተያየት መሆኑ ቶሎ ገባው "
“ አይደለም ” አለችው ራሷን ነቅንቃ ። “የሥቃይ ቤት ነው እኔም ከእንግዲህ ከዚህ ቤት መኖር አልችልም " ወዴት አባቴ እንደምሔድ ዛሬ ሌሊት ሳስብ
አንዳችም ብልሃት ሳላገኝ ተጎልቸ አደርኩ " እኔ በዚህ ሰፊ ዓለም አንድም ሁነኛ ሰው የለኝም "
ከልጆች ፌት ምስጢር መጫወት ተገቢ አይደለም ከሚገምቱት በላይ መስማትና ማስተዋል እንደሚችሉ ማወቁ ተገቢ ነው ትንንሽ ጋኖች ትልልቅ ጆሮዎች
አሏቸው የሚባለው አነጋገር የሚያስገርም ሐቅ ነው ሎርድ ቬን አንገቱን ቀና አድርጎ ሚስተር ካርላይልን ሽቅብ ይመለከተው ጀመር "
“ ሳቤላ “ ኮ ከኛ ቤት እወጣለሁ ብላ ዛሬ ጧት ነገረችኝ " ለምን እንደሆነ ልንገርዎት ? ትናንት ማታ እማማ ተናድዳ ስለ መታቻት ነው "
“ ዝም በል ዊልያም ” ብላ አቋረጠችው ሳቤላ „ “ ሁለት ጊዜ በጥፌ መታቻት ጉንጮ ላይ ” አለና ልጁ ነገሩን በመቀጠል “ሳቤላም አለቀሰች እኔም ጮህኩ በዚህ ጊዜ እማማ እኔንም አጮለችኝ " ልጆች ለመመታት ነዉ የተፈጠሩት ትላለች ሞግዜቴ። ሻይ ስንጠጣ ማርቨል መጥታ ለሞግዚቴ ነገረቻት እማማ ሳቤላን የምትመታት እኮ ሳቤላ በመልክ ስለምትበልጣት ...>>
ሳቤላ ፡ አፉን ይዛ አቋረጠችውና አንዲት ሠራተኛ ጠርታ ወደ ልጆች ክፍል አስወሰደችው : የሚስተር ካርላይል ዐይኖች በንዴትና በኅዘን ብርዝ አሎ „ “ እውነት ነው ? ” አላት ፊቷን ወደሱ ምልስ ስታደርግ “ እውነትም ሁነኛ ሰው ያስፈልግሻል።
ዕድሌ የጣለብኝን ዕጣ መቀበል አለብኝ ' ሲቀር ሲውል ሎርድ ማውንት እስቨርን እስኪመለስ ድረስ ”
“ ከዚያ በኋላስ ምን ትሆኛለሽ ? ''
ከዚያ በኋላ የምሆነውን ምንም አላውቅም ” አለችው ልማደኛው እንባዋ ልትቈጣጠረው ከማትችለው ፍጥነት በላይ እየገነፈለ „ “ እሱ ለኔ የሚሰጠኝ ሌላ ቤት የለውም ። እኔ ደግሞ ከወይዘሮ ማውንት እስቨርን ጋር አብሬ መኖር አልችልም "
መንፈሴን ድቅቅ አድርጋ እንደ ስበረችው ሁሉ አሁንም ልቤን ታፈሰዋለች » እኔ በሷ ይህን ያሀል መበደል የሚገባኝ ስው አልነበርኩም ... ሚስተር ካርላይል
በርግጥ አልነበርሽም ” አላት ሚስተር ካርላይል “ አሁን ምን ላድርግልሽ እችላለሁ ? ''
“ አሁን አንተም ሆንክ ሌላ ምንም ሊያደርግልኝ አይችልም : ”
“ አንቺን መርዳት የምችልበት መንገድ ባገኝ በጣም ደስ ይለኝ ነበር " መቸም ኢስትሊንም ላንቺ የደስታ ቤት አልነበረም ነገር ግን ከለቀቅሺው ወዲህ የባሰ ተጐሳቁለሻል
የደስታ ቤት አልነበረም አልከኝ ? ” አለችው የኢስትሊን የኑሮ ትዝታ ድቅን እያለባት “ ኧረ እሱስ ነበረ እንግዲህም እንደሱ ደስ የሚል ኑሮ የማገኝ አይመስለኝም ሚስርተር ካርላይል ኢስትሊንን አቃለህ አትንገረኝ " ምነው አሁን
እነዚያ ያሳለፍኩዋቸው የመከራ ወሮች ወደ ሕልም በተለወጡና አባቴን በሕይወቱ አግኝቸው ኢስትሊን ውስጥ እንደ ዱሮአችን በሰላም ስኖር ከእንቅልፌ በነቃሁ . .
“ ወደ ኢስትሊን የምትመለሽበት አንድ መንገድ ብቻ አለ ” አላት መንፈሱ ጭንቅ ጭንቅ እያለው ልቡ በጣም እየመታ እጂዋን ያዝ አድርጎ ምናልባትም ሳይታወቀው ሊሆን ይችላል · ጣቶቹ ከጣቶቿ ጋር እየተጫወቱ " ንግግሬ የሚያስከፋሽ ከሆነ መልሽኝ : በጥፋቴም ይቅርታ አድርጊልኝ "የኢስትሊን እመቤት ሆነሽ
እንድትመለሽበት ብጠይቅሽ ድፍሬት ይሆንብኛል ? ”
ምን ለማለት እንደ ፈለገ ፍጹም አልገባትም „ “እመቤት ሁኜ ወደ ኢስትሊን መመለስ ? ” አለችው ድንግጥ ብላ "
“ አዎን ' የኢስትሊን እመቤት የኔ ባለቤት ሆነሽ " ብሎ መላሰላት
አሁን ገባት መገረምም መደንገጥም †ነባበሩባት " በርግጥ ሚስተር ካርላይል
ብዙ ውለታ የዋለላት ከደግንቱ እንከን ያላገኘችበት ሰው ስለነበር ትወደው ነበር ሚስቱ የመሆን ጉዳይግን እሱ አፍ አውጥቶ እስከ ጠየቀበት ሰዓትድረስ አሰባው
አታውቅም ደነገጠችም ለዚሁ ነበር እጅዋንም ከእጁ አስለቅቃ ሊሆን እንደማይችል ልትነግረው ቃጣትና እጅዋን ሳብ ስታደርግ እሱ ደግሞ ጠበቅ አደረጋት።
የመናገር ፈራ ተባው ለቀቀው " ጠቅላላ ስለሷ ያለውን ስሜት የትዳሩን ዓላማና የፍቅሩን ነገር በማይስቱና ልብን በሚወጉ የቃላት ቀስት ነደፋት ልብን በሚነካ ንግግር ሐሳቡን በሙሉ በምታውቀው ሐቀኝነቱ ግልጽልጽ አድርጎ አጫታት ሁለቱ በዚህ ሁኔታ እንዳሉ ወይዘሮ ማውንት እስቨርን ገባች ደነገጠችና ምንም ሳትናገር በሐሳቧ ብቻ ላቀረበችው ጥያቄ መልስ የምትጠብቅ
ይመስል ቀጥ ብላ ቆመች።
ሚስተር ካርላይል ሳቤላን ያዳነ መሰለውና ራሱን ለማስተዋወቅ ወደሷ ቀረብ ሲል ሳቤላ ደግሞ ተረጋጋችና “ ወይዘሮ ማውንት እስቨርን ” ብላ አስተዋወቀች ,
ሎርድ ማውንት እስቨርን ባለመኖራቸው በጣም አዝናለሁ " እሳቸው ያውቁኝ ነበር እኔ ሚስተር ካርላይል እባላለሁ ” አላት "
“እኔም ስለአንተ ሰምቻለሁ " አለችው ሸጋ መልኩን እየቃኘችና አክብሮቴን ለማትወዳት ሴት ሲሰጥ በማየቷ ቅር እያላት “ከወይዘሮ ሳቤላ ቬን ጋር ይኸን ያህል የቀረበ ወዳጅነት እንዳላችሁ ግን አልሰማሁም " ”
“ እስካሁን እንኩዋን ለእርስዎ የመሰለዎትን ያህል የጠና ወዳጅነት አልነበረንም” አላት ወንበር ጠጋ ካዪረገላት በኋላ ለራሱም ሌላ እያስተካከለ „ “ አሁን ግን ወዳጅነታችንን የጠና ለማድረግ ሚስቴ እንድትሆን እየለመንኳት ነበር '
እመቤቲቱ ከዚያች ከምትጠላት ልጅ የምትላቀቅበት ፍንጭ በማግኘቷ የከፋው ፊቷ የደስታ ብርሃን ፈነጠቀበት " ሚስተር ካርላይልን እንደ ትልቅ ባለውለታዋ
አድርጋ አየችው ።
“ግድ የለሹ አባቷ ያለምንም አለኝታ ጥለዋት እንደሞቱ • አንተም ታውቃለህ ስለዚህ እንደዚህ ያለ ከፍተኛ የጋብቻ ጥያቄ ሲቀርብላት ሳቤላ በደስታ መቀበል አለባት " ደግሞም እንደ ሰማሁት ኢስትሊን በጣም የሚያምር ቦታ ነው ይባላል
አለችውና ፊቷን ወደ ሳቤላ መልሳ “ ለመሆኑ የሷ መልስ ምንድነው? ” ብላ ጠየቀችው።
ኅቤላ ለሷ በቀጥታ መልስ እንደ መስጠት ራሷን ዝቅ እንደ ማድረግ ቆጠረችውና ሚስተር ካርላይልን 'እንዳስብበት ጥቂት ሰዓት ልትሰጠኝ ትችላለህ ? '' አለችው "
“ በነገሩ በደንብ ብታስቢበት ለኔም በጣም ደስ ይለኛል " ስለዚህ ከሰዓት በኋላ እመለሳለሁ ” ብሏት ሔደ ።
ሚስተር ካርይል ከወይዘሮ ማውንት እስቨርን ጋር ሲነጋገር ሳቤላ ከክፍሏ ግብታ ብቻዋን በጣም ግራ የሚያጋባ ሙግት ጀመረች " ሳቤላ ከልጅ እምብዛም
አትሻልም ነበር አስተሳሰቧና ክርክሯ ሁሉ እንዶ ልጅ ላይ ላዩን እንጂ ጥልቀትና ብስለት አልነበረውም " ሚስተር ካርላይል የተራ ቤተሰብ ልጅ መሆኑንና እንደሷ ከትልቅ ሰው ባለወለዱ አቻዋ ያለመሆኑን ነገር አላሰበችውም " ኢስትሊን ለዘለቄታ መኖሪያነት ጥሩ ቦታ ነበር " በመጠን በውበትና በጠቃሚነትም ረገድ
አሁን ከምትኖርበት ከካስል ማርሊንግ በጣም የላቀ ነበር " ነገር ግን ኢስትሊንን የሚስተር ካርላይል ሚስት ሆና ስትገባበት የሎርድ ማውንት እስቨርን ልጅ ሆና እንደ ኖረችበት እንደማይሆንላት አላሰበችውም " ተወልዳ ካደገችበት ድምቀት
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
....አንድ ጊዜ የማጠቃለያ እንቅስቃሴዬን ስሰራ፣ ክሪስ እንግዳ ስሜት ፊቱ ላይ እየተነበበ ሲመለከተኝ አየሁ: በቅርቡ አስራ አምስት አመት ልደቱን ያከብራል፡ እንዴት ይሆናል? ትልቅ ሰው እንጂ በጭራሽ ልጅ አይመስልም
ከልጅነት በፍጥነት እየወጣ እንደሆነ የሚናገሩት እነዚያ አይኖቹ ናቸው?ከዚያ ወደ ክሪስ ሄድኩና እጆቼን ወደ እሱ ዘርግቼ “ክሪስ ና ከእኔ ጋር እንደንስ፧ እንዴት እንደሆነ ላስተምርህ?” አልኩት።በመገረም ፈገግ አለና ጭንቅላቱን በመነቅነቅ እንደማይችል ነገረኝ፡ “ባሌት ዳንስ ለእኔ አይሆንም ቫልስ ግን መማር እፈልጋለሁ” አለ፡ አሳቀኝ በዚያን ወቅት የነበረን ብቸኛው የቫልስ ሙዚቃ አሮጌ ነበር፡ ወደ ማጫወቻው እየፈጠንኩ ሄጄ እየተጫወተ የነበረውን አወጣሁና የቫልሱን ከተትኩት ክሪስ ገልጃጃ ሆኖ ነበር የያዘኝ በሚያስቅ አይነት አያያዝ ነበር። በዚያ ላይ ያፈረ ይመስላል ደጋግሞ እየተደነቃቀፈ ሮዝ ቀለም ያለው ሹል ጫማዬ ላይ ይቆማል። ቀላል የሆኑትን እንቅስቃሴዎች ላለመሳሳት ጠንክሮ መሞከሩ ልብ የሚነካ ነበር ተሰጥኦው አእምሮው ውስጥና በጥበበኛ እጆቹ ክህሎት
ላይ እንጂ አንዳቸውም ወደ ቅልጥሞቹና ወደ እግሮቹ እንዳልወረዱ ልነግረው
አልቻልኩም::
በመጨረሻ እናታችን የሚያምሩ ላባዎች ያሉበት ጠባብ ኮፍያ፣ ነጭ ጫማና ቀሚስ ያለበት የዳንስ ልብስ ይዛ በበሩ ስትገባ በከባዱ ተነፈስኩ ፍቅር፣ ተስፋና ደስታ በአንድ ሀምራዊ ሪባን በታሰረበት ትልቅ ካርቶን በኩል
በጣም በሚያስብልኝ አንድ ሰውና ሀሳቡን ውስጧ በከተተው በሌላ ሰው አማካይነት ወደ ፎቁ የመጣ ይመስል ነበር በመጨረሻ ክሪስን ሌሎች ዳንሶችን ላስተምረው ስል ተቃወመኝ፡፡ “እንዳንቺ ሁሉንም የዳንስ አይነቶች መማር አያስፈልገኝም: ምክንያቱም እኔ መድረክ ላይ አልደንስም የምፈልገው ከሴት ጋር የመደነስ አጋጣሚ ቢመጣ መቀለጃ
እንዳልሆን ብቻ ነው:" አለኝ፡
“ክሪስ፣ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ በየአመቱ የዳንስ አይነቶች ልክ እንደ ልብስ ፋሽን ይለዋወጣሉ፡ ስለዚህ ከጊዜው ጋር መሄድ አለብህ አለበለዚያ
ማንም ሴት አታፈቅርህም::”
“ልታፈቅረኝ የምትችል ሴት አትኖርም:”
እንደዚያ አይነት ሰው ፋሽን ያለፈበት ቢሆንም እሱ ግን ማንም ሰው ለራሱ ያለውን ምስል እንዲለውጥ እንዲያስገድደው አይፈቅድም የራሱ ሰው
በመሆኑ እወደዋለሁ የኔ ሰር ክሪስቶፈር
ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ እንደሆንን ወቅቶች ለወጥን፡ የለጠፍናቸውን አበቦች አውርደን በበልግ ቅጠሎች ተካናቸው ክረምት ሲመጣም እዚህ
የምንሆን ከሆነ በረዶ መጣል ሲጀምር የቆራረጥናቸውን ነጫጭ ንድፎች እንሰቅላቸዋለን፡፡
ክሪስ መፅሀፍ በማያነብበት ጊዜ ስዕሎችን በውሀ ቀለም ይስላል በበረዶ የተሸፈኑ ኮረብታዎች፣ የበረዶ ሸርታቴ የሚጫወቱ ሰዎች የሚያቋርጧቸውን ሀይቆች፣ በረዶ ውስጥ የተቀበሩ ቢጫና ሮዝ ትንንሽ ቤቶችና ከጭስ መውጫው ውስጥ የተጥመለመለ ጭስ ሲወጣ የሚያሳይ ይሰራል። ሲጨርስ የመስኮቱን ጥቁር ፍሬም ቀለም ይቀባና ስዕሉን ግድግዳው ላይ ሲለጥፈው ደስ የሚል እይታ ያለው ክፍል ይሆንልናል
አንድ ጊዜ እኔና ክሪስ አሮጌው ፍራሽ ላይ ጎን ለጎን ተጋድመን እያወራን ነበር ነፃና ሀብታም ስንሆን ስለምንኖረው ኑሮ እቅድ ስናወጣ “በዓለም ዙሪያ እንጓዛለን፤ በጣም ቆንጆ፣ አስተዋይና የምትስብ ሴት አገኝና ፍቅር ይይዘኛል። ልጅቷ ታማኝ፣ ቤት አያያዝ ላይ ጎበዝ የሆነች፣ የማትጨቃጨቅ፣የማታማርር፣ የማትጮህ... ትሆናለች” ብሎ ሲናገር የበታችነት እንዲሰማኝ
አደረገኝ የወደፊት ትዳር ጠያቂዎቼን የምመዝንበት ደረጃ እያወጣልኝ እንደሆነ አውቄያለሁ: ታዲያ እንደ ክሪስ ያለ ወንድን ፍላጎት ማሟላት የምችለው እንዴት ነው?
ክሪስ… ይቺ ጎበዝ፣ ማራኪ፣ እውቀት ያላትና ቆንጆ ሴት ያልካት አንድ ትንሽ ጉድለት እንኳን የላትም?”
“ለምን ጉድለት ይኖራታል?”
“ለምሳሌ እናታችንን ውሰድ። ምናልባት ጎበዝ ከሚለው በስተቀር በሁሉም ነገር የምታስባት አይነት ሴት ናት።”
“እናታችን ደደብ አይደለችም!” ተከላከለላት᎓ “በተሳሳተ አይነት አካባቢ ስላደገች ብቻ ነው! በልጅነቷ ዝቅ ተደርጋ ትታይ ነበር። ሴት በመሆኗ ዝቅተኝነት
እንዲሰማት አድርገዋታል"
በበኩሌ ለተወሰኑ አመታት ታዋቂ ዳንሰኛ ከሆንኩኝ በኋላ ለማግባት
ስፈልግ ክሪስ ጋ ወይም አባቴ ጋ ካልደረሰ ምን እንደማደርግ አላውቅም።መልከመልካም እንደሚሆን አውቃለሁ- ምክንያቱም ልጆቼ ቆንጆዎች
እንዲሆኑ እፈልጋለሁና። ጎበዝ እንዲሆን እፈልጋለሁ አለበለዚያ ላላከብረው እችላለሁ የመተጫጫ የአልማዝ ቀለበቱን ከመቀበሌ በፊት ቁጭ እንዲል
አደርግና ጨዋታ እንጫወታለን፡ ደጋግሜ ካሸነፍኩት ፈገግ እልና ጭንቅላቴን ነቅንቄ ቀለበቱን ወስዶ የገዛበት ሱቅ እንዲመልሰው እነግረዋለሁ
ማሰሮ ውስጥ የተተከሉት አበቦቻችን ጠወለጉ ለአትክልቶቻችን የፍቅር
እንክብካቤ እናደርግላቸዋለን እናወራቸዋለን፣መምሰል አቁሙ እንላቸዋለን አንገቶቻቸውን ቀጥ እናደርግላቸዋለን ከሁሉም በላይ በጣም ጤናማ የሆነውን የምስራቅ የጠዋት ፀሀይ ያገኙ ነበር።ቅጠሎቹ ግን እየሞቱ ነበር‥. ቢጫ፡ እየሆኑ ይሄዱ ጀመር ።
እያደር ኮሪና ኬሪ ውጪ ለመውጣት መጠየቃቸውን አቆሙ፡ ኬሪ በትንንሽ
እጆቿ ቡጢ ጨብጣ በሩን መደብደቧን ተወች:: ኮሪ በእግሮቹ መሬቱን መደብደብ አቁሞ ትንንሽ የእግሮቹን ጣቶች የማያጣብቃቸውን ለስላሳ
ጫማዎች ማድረግ ጀመረ
አሁን የሚያገኙት ብቸኛው “ውጪ” ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ የሚገኘው የአትክልት ስፍራ ብቻ መሆኑን ተቀበሉ። ምስኪን መንትዮቹ...ከጊዜ በኋላ በሚያሳዝን ሁኔታ ከዚህ ከተቆለፍንበት ክፍል ውጪ ሌላ አለም ከነመኖሩም ይረሳሉ
ልጆች ለማደግ የፀሀይ ብርሀን ያስፈልጋቸዋል እኛ ማድረግ ያለብን እየሞቁ ያሉትን ተክሎች መመልከትና የጣሪያው ስር ክፍል ውስጥ የአትክልት ቦታችን ላይ ያደረግነውን ነገር መታዘብ ብቻ ነው: ፀሀይዋ እኛ ክፍል
ውስጥ ስለማትገባ ፀሀይ ለማግኘት ፍራሾችን መስኮቱ ስር እንከምርና ላዩ ላይ እንሆናለን
በአጭር ጊዜ ውስጥ ፀሀዩዋ መስኮታችን ጋ ስትደርስ ምንም ሳናፍር ልብሶቻችንን ሁሉ አወላልቀን ፀሀይ እንሞቃለን፡፡ የእያንዳንዳችንን ልዩነት
አየንና ስለነገሩ ብዙም ሳናስብ ያደረግነውን በግልፅ ለእናታችን ነገርናት ምክንያቱም የፀሀይ ብርሀን በማጣት መሞት የለብንምና፡ እናታችን እይታዋን
ከክሪስ ወደ እኔ እያደረገች ደካማ ፈገግታ አሳየችን፡ “ምንም አይደለም ግን አደራ አያታችሁ እንዳትሰማ! ሁላችሁም እንደምታውቁት እሷ በዚህ ደስ
አይላትም” አለች።
መጀመሪያ ክሪስን ከዚያ እኔን እያፈራረቀች ትመለከተን የነበረው ንፁሁነታችንን የሚያሳይ ወይም ስለ ፆታዊ ግንኙነቶች መንቃታችንን የሚያመለክት ምልክት ለመፈለግ መሆኑን አውቄያለሁ መንትዮቹ እርቃናቸውን ሆነው እንደ ህፃናት መጫወት ይወዳሉ አንድ
ቀን ኬሪ “ለምን ክሪስ…?” ብላ ጠየቀች᎓ እሱና ኮሪ ያላቸውና እሷ የሌላትን የሰውነት ክፍል እየጠቆመች። ክሪስ ትክክለኛና እውነተኛ የሆነውን መልስ
ለመመለስ በመሞከር “ሁሉም ወንድ ፍጥረታት የመራቢያ አካላቸው የሚገኘው
ከውጪ ነው: የሴቶች ደግሞ ከውስጥ ስለሆነ ነው። ወላጆቻችን እርቃን ሰውነታችንን ልክ እንደ አይኖቻችንና ፀጉራችን ተቀብለውታል ስለዚህ ባለን
መደሰት አለብን” አላት
“ወንድ ወፎች ደግሞ ልክ እንደ ሴቶች የመራቢያ አካላቸው ያለው ከውስጥ በኩል ነው: አለች ኬሪ
ተገርሜ “እንዴት አወቅሽ?" ብዬ ጠየቅኳት᎓
“በቃ አወቅኩ፡”
“መፅሀፍ ላይ አንብበሽ ነው?”
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ
....አንድ ጊዜ የማጠቃለያ እንቅስቃሴዬን ስሰራ፣ ክሪስ እንግዳ ስሜት ፊቱ ላይ እየተነበበ ሲመለከተኝ አየሁ: በቅርቡ አስራ አምስት አመት ልደቱን ያከብራል፡ እንዴት ይሆናል? ትልቅ ሰው እንጂ በጭራሽ ልጅ አይመስልም
ከልጅነት በፍጥነት እየወጣ እንደሆነ የሚናገሩት እነዚያ አይኖቹ ናቸው?ከዚያ ወደ ክሪስ ሄድኩና እጆቼን ወደ እሱ ዘርግቼ “ክሪስ ና ከእኔ ጋር እንደንስ፧ እንዴት እንደሆነ ላስተምርህ?” አልኩት።በመገረም ፈገግ አለና ጭንቅላቱን በመነቅነቅ እንደማይችል ነገረኝ፡ “ባሌት ዳንስ ለእኔ አይሆንም ቫልስ ግን መማር እፈልጋለሁ” አለ፡ አሳቀኝ በዚያን ወቅት የነበረን ብቸኛው የቫልስ ሙዚቃ አሮጌ ነበር፡ ወደ ማጫወቻው እየፈጠንኩ ሄጄ እየተጫወተ የነበረውን አወጣሁና የቫልሱን ከተትኩት ክሪስ ገልጃጃ ሆኖ ነበር የያዘኝ በሚያስቅ አይነት አያያዝ ነበር። በዚያ ላይ ያፈረ ይመስላል ደጋግሞ እየተደነቃቀፈ ሮዝ ቀለም ያለው ሹል ጫማዬ ላይ ይቆማል። ቀላል የሆኑትን እንቅስቃሴዎች ላለመሳሳት ጠንክሮ መሞከሩ ልብ የሚነካ ነበር ተሰጥኦው አእምሮው ውስጥና በጥበበኛ እጆቹ ክህሎት
ላይ እንጂ አንዳቸውም ወደ ቅልጥሞቹና ወደ እግሮቹ እንዳልወረዱ ልነግረው
አልቻልኩም::
በመጨረሻ እናታችን የሚያምሩ ላባዎች ያሉበት ጠባብ ኮፍያ፣ ነጭ ጫማና ቀሚስ ያለበት የዳንስ ልብስ ይዛ በበሩ ስትገባ በከባዱ ተነፈስኩ ፍቅር፣ ተስፋና ደስታ በአንድ ሀምራዊ ሪባን በታሰረበት ትልቅ ካርቶን በኩል
በጣም በሚያስብልኝ አንድ ሰውና ሀሳቡን ውስጧ በከተተው በሌላ ሰው አማካይነት ወደ ፎቁ የመጣ ይመስል ነበር በመጨረሻ ክሪስን ሌሎች ዳንሶችን ላስተምረው ስል ተቃወመኝ፡፡ “እንዳንቺ ሁሉንም የዳንስ አይነቶች መማር አያስፈልገኝም: ምክንያቱም እኔ መድረክ ላይ አልደንስም የምፈልገው ከሴት ጋር የመደነስ አጋጣሚ ቢመጣ መቀለጃ
እንዳልሆን ብቻ ነው:" አለኝ፡
“ክሪስ፣ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ በየአመቱ የዳንስ አይነቶች ልክ እንደ ልብስ ፋሽን ይለዋወጣሉ፡ ስለዚህ ከጊዜው ጋር መሄድ አለብህ አለበለዚያ
ማንም ሴት አታፈቅርህም::”
“ልታፈቅረኝ የምትችል ሴት አትኖርም:”
እንደዚያ አይነት ሰው ፋሽን ያለፈበት ቢሆንም እሱ ግን ማንም ሰው ለራሱ ያለውን ምስል እንዲለውጥ እንዲያስገድደው አይፈቅድም የራሱ ሰው
በመሆኑ እወደዋለሁ የኔ ሰር ክሪስቶፈር
ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ እንደሆንን ወቅቶች ለወጥን፡ የለጠፍናቸውን አበቦች አውርደን በበልግ ቅጠሎች ተካናቸው ክረምት ሲመጣም እዚህ
የምንሆን ከሆነ በረዶ መጣል ሲጀምር የቆራረጥናቸውን ነጫጭ ንድፎች እንሰቅላቸዋለን፡፡
ክሪስ መፅሀፍ በማያነብበት ጊዜ ስዕሎችን በውሀ ቀለም ይስላል በበረዶ የተሸፈኑ ኮረብታዎች፣ የበረዶ ሸርታቴ የሚጫወቱ ሰዎች የሚያቋርጧቸውን ሀይቆች፣ በረዶ ውስጥ የተቀበሩ ቢጫና ሮዝ ትንንሽ ቤቶችና ከጭስ መውጫው ውስጥ የተጥመለመለ ጭስ ሲወጣ የሚያሳይ ይሰራል። ሲጨርስ የመስኮቱን ጥቁር ፍሬም ቀለም ይቀባና ስዕሉን ግድግዳው ላይ ሲለጥፈው ደስ የሚል እይታ ያለው ክፍል ይሆንልናል
አንድ ጊዜ እኔና ክሪስ አሮጌው ፍራሽ ላይ ጎን ለጎን ተጋድመን እያወራን ነበር ነፃና ሀብታም ስንሆን ስለምንኖረው ኑሮ እቅድ ስናወጣ “በዓለም ዙሪያ እንጓዛለን፤ በጣም ቆንጆ፣ አስተዋይና የምትስብ ሴት አገኝና ፍቅር ይይዘኛል። ልጅቷ ታማኝ፣ ቤት አያያዝ ላይ ጎበዝ የሆነች፣ የማትጨቃጨቅ፣የማታማርር፣ የማትጮህ... ትሆናለች” ብሎ ሲናገር የበታችነት እንዲሰማኝ
አደረገኝ የወደፊት ትዳር ጠያቂዎቼን የምመዝንበት ደረጃ እያወጣልኝ እንደሆነ አውቄያለሁ: ታዲያ እንደ ክሪስ ያለ ወንድን ፍላጎት ማሟላት የምችለው እንዴት ነው?
ክሪስ… ይቺ ጎበዝ፣ ማራኪ፣ እውቀት ያላትና ቆንጆ ሴት ያልካት አንድ ትንሽ ጉድለት እንኳን የላትም?”
“ለምን ጉድለት ይኖራታል?”
“ለምሳሌ እናታችንን ውሰድ። ምናልባት ጎበዝ ከሚለው በስተቀር በሁሉም ነገር የምታስባት አይነት ሴት ናት።”
“እናታችን ደደብ አይደለችም!” ተከላከለላት᎓ “በተሳሳተ አይነት አካባቢ ስላደገች ብቻ ነው! በልጅነቷ ዝቅ ተደርጋ ትታይ ነበር። ሴት በመሆኗ ዝቅተኝነት
እንዲሰማት አድርገዋታል"
በበኩሌ ለተወሰኑ አመታት ታዋቂ ዳንሰኛ ከሆንኩኝ በኋላ ለማግባት
ስፈልግ ክሪስ ጋ ወይም አባቴ ጋ ካልደረሰ ምን እንደማደርግ አላውቅም።መልከመልካም እንደሚሆን አውቃለሁ- ምክንያቱም ልጆቼ ቆንጆዎች
እንዲሆኑ እፈልጋለሁና። ጎበዝ እንዲሆን እፈልጋለሁ አለበለዚያ ላላከብረው እችላለሁ የመተጫጫ የአልማዝ ቀለበቱን ከመቀበሌ በፊት ቁጭ እንዲል
አደርግና ጨዋታ እንጫወታለን፡ ደጋግሜ ካሸነፍኩት ፈገግ እልና ጭንቅላቴን ነቅንቄ ቀለበቱን ወስዶ የገዛበት ሱቅ እንዲመልሰው እነግረዋለሁ
ማሰሮ ውስጥ የተተከሉት አበቦቻችን ጠወለጉ ለአትክልቶቻችን የፍቅር
እንክብካቤ እናደርግላቸዋለን እናወራቸዋለን፣መምሰል አቁሙ እንላቸዋለን አንገቶቻቸውን ቀጥ እናደርግላቸዋለን ከሁሉም በላይ በጣም ጤናማ የሆነውን የምስራቅ የጠዋት ፀሀይ ያገኙ ነበር።ቅጠሎቹ ግን እየሞቱ ነበር‥. ቢጫ፡ እየሆኑ ይሄዱ ጀመር ።
እያደር ኮሪና ኬሪ ውጪ ለመውጣት መጠየቃቸውን አቆሙ፡ ኬሪ በትንንሽ
እጆቿ ቡጢ ጨብጣ በሩን መደብደቧን ተወች:: ኮሪ በእግሮቹ መሬቱን መደብደብ አቁሞ ትንንሽ የእግሮቹን ጣቶች የማያጣብቃቸውን ለስላሳ
ጫማዎች ማድረግ ጀመረ
አሁን የሚያገኙት ብቸኛው “ውጪ” ጣሪያው ስር ያለው ክፍል ውስጥ የሚገኘው የአትክልት ስፍራ ብቻ መሆኑን ተቀበሉ። ምስኪን መንትዮቹ...ከጊዜ በኋላ በሚያሳዝን ሁኔታ ከዚህ ከተቆለፍንበት ክፍል ውጪ ሌላ አለም ከነመኖሩም ይረሳሉ
ልጆች ለማደግ የፀሀይ ብርሀን ያስፈልጋቸዋል እኛ ማድረግ ያለብን እየሞቁ ያሉትን ተክሎች መመልከትና የጣሪያው ስር ክፍል ውስጥ የአትክልት ቦታችን ላይ ያደረግነውን ነገር መታዘብ ብቻ ነው: ፀሀይዋ እኛ ክፍል
ውስጥ ስለማትገባ ፀሀይ ለማግኘት ፍራሾችን መስኮቱ ስር እንከምርና ላዩ ላይ እንሆናለን
በአጭር ጊዜ ውስጥ ፀሀዩዋ መስኮታችን ጋ ስትደርስ ምንም ሳናፍር ልብሶቻችንን ሁሉ አወላልቀን ፀሀይ እንሞቃለን፡፡ የእያንዳንዳችንን ልዩነት
አየንና ስለነገሩ ብዙም ሳናስብ ያደረግነውን በግልፅ ለእናታችን ነገርናት ምክንያቱም የፀሀይ ብርሀን በማጣት መሞት የለብንምና፡ እናታችን እይታዋን
ከክሪስ ወደ እኔ እያደረገች ደካማ ፈገግታ አሳየችን፡ “ምንም አይደለም ግን አደራ አያታችሁ እንዳትሰማ! ሁላችሁም እንደምታውቁት እሷ በዚህ ደስ
አይላትም” አለች።
መጀመሪያ ክሪስን ከዚያ እኔን እያፈራረቀች ትመለከተን የነበረው ንፁሁነታችንን የሚያሳይ ወይም ስለ ፆታዊ ግንኙነቶች መንቃታችንን የሚያመለክት ምልክት ለመፈለግ መሆኑን አውቄያለሁ መንትዮቹ እርቃናቸውን ሆነው እንደ ህፃናት መጫወት ይወዳሉ አንድ
ቀን ኬሪ “ለምን ክሪስ…?” ብላ ጠየቀች᎓ እሱና ኮሪ ያላቸውና እሷ የሌላትን የሰውነት ክፍል እየጠቆመች። ክሪስ ትክክለኛና እውነተኛ የሆነውን መልስ
ለመመለስ በመሞከር “ሁሉም ወንድ ፍጥረታት የመራቢያ አካላቸው የሚገኘው
ከውጪ ነው: የሴቶች ደግሞ ከውስጥ ስለሆነ ነው። ወላጆቻችን እርቃን ሰውነታችንን ልክ እንደ አይኖቻችንና ፀጉራችን ተቀብለውታል ስለዚህ ባለን
መደሰት አለብን” አላት
“ወንድ ወፎች ደግሞ ልክ እንደ ሴቶች የመራቢያ አካላቸው ያለው ከውስጥ በኩል ነው: አለች ኬሪ
ተገርሜ “እንዴት አወቅሽ?" ብዬ ጠየቅኳት᎓
“በቃ አወቅኩ፡”
“መፅሀፍ ላይ አንብበሽ ነው?”
#ጠላፊዎቹ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ሄሪ ፍርድ ቤቱ የጣለበትን የዋስ ክፍያ ሳያስይዝ፣ በሃሰት ፓስፖርትና
ስም ተጠቅሞ አሜሪካዊ ነኝ እያለ እንዳልመጣ አሁን ሌባ መሆኑን የምታውቅ ልክ በስሙ ስትጠራው አመዱ ቡን አለ፡፡
ካገር ያሰደደው አስከፊ ነገር ሁሉ ዓይኑ ላይ ድቅን አለበት፡ የፍርድ ቤቱ እሰጥ አገባ፣ እስር ቤት የቆየባቸው ቀናትና የግዴታ ውትድርና
አገልግሎት፡
በኋላ ግን ዕድለኛነቱ ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡
ሄሪ ልጅቷ ግራ እንደገባት አየ፡፡ ስሟን ለስታወስ ሞከረና መጣለት
እመቤት ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ፡
ልጅቷ በመገረም አፈጠጠችበት።
‹‹ስሜ ሄሪ ቫንዴርፖስት ነው›› አላት፤ ካንቺ ይልቅ እኔ የተሻለ አስታውሳለሁ፡ አንቺ ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ አይደለሽም? እንዴነት ነሽ?››
‹‹ደህና ነኝ›› አለች በድንጋጤ ደንዝዛ
ለሰላምታ እጁን ሲዘረጋላት ልትጨብጠው እጇን ስትሰድ መጨበጡን
ትቶ ‹‹ከዚህ በፊት ፖሊስ ጣቢያ እንዳላየሽኝ ሁኚ፧ እኔም እንዲሁ አደርጋለሁ›› አላት፡፡
ግራ መጋባቷ ሲለቃት ፈገግ አለች፡፡ የነገራት ገባትና ‹‹እንዴ ምን ነካኝ
ሄሪ ቫንዴርፖስት›› አለች፡
ሄሪ አሁን ቀለል አለው፡፡ በዓለም ላይ መቼም እንደኔ እድለኛ የለም አለ በሆዱ፡፡
ማርጋሬትም ‹የሆኖ ሆኖ የት ነበር የምንተዋወቀው?›› ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አንድ ዳንስ ቤት የተገናኘን ይመስለኛል›› አላት፡፡
‹‹ልክ ነው እዚያ ነው የማውቅህ›› አለች
በዚህ ጊዜ ፈገግ አለ፡፡
የሴራው ተካፋይ አደረጋት፡፡
በመቀጠልም ‹‹ቤተሰቦቼን ላስተዋውቅህ›› አለችና ‹‹እማማ አባባ ሚስተር ቫንዴርፖስትን ተዋወቁት ከ. . . ስትል ከአፏ ነጥቆ ‹‹ከአሜሪካ
ፔንሲልቫኒያ›› አለና ንግግሯን ጨረሰላት፡፡
ፔንሲልቫንያ የሚለው ቃል ካፉ ሲወጣ ዕድሉን ረገመ፡፡ ፔንሲልቫኒያ የት እንደሚገኝ አያውቅም፡፡
‹‹ይቺ እናቴ ናት፤ ይሄ አባቴ፤ ይሄ ደግሞ ወንድሜ ነው›› በማለት በማዕረግ ስማቸው አስተዋወቀችው:: ሄሪ ሁሉንም በዝና ያውቃቸዋል፡ ሄሪ የማርጋሬትን ቤተሰቦች ልባዊ በሆነ በአሜሪካውያን ተግባቢነት ባህሪ ሰላምታ
ሰጣቸው፡፡
ሎርድ ኦክሰንፎርድ እንደልማዳቸው በትዕቢት ተጀንነው ተኮፍሰዋል:
ሄሪ እናቷን ማነጋገር መረጠና ‹‹እንደም ነዎት የኔ፧ እመቤት? የተሰማራሁት
በእንቁ ጌጣጌጥ ንግድ ላይ ነው፤ እርስዎም በዓለም ላይ አለ የሚባል የዕንቁ ስብስብ እንዳለዎት ሰምቻለሁ›› አላቸው፡፡
‹‹እውነት ነው፤ ዕንቁ እወዳለሁ›› አሉት፡፡
ሄሪ የእመቤት ኦክሰንፎርድን የአሜሪካውያን የአነጋገር ቅላጼ ሲሰማ ቀልቡ ተገፈፈ፡፡ ስለእኚህ እመቤት መጽሔት ላይ አንብቧል፡፡ሴትየዋ እንግሊዛዊት ይመስሉት ነበር፡፡ መጽሔቶች ላይ ስለ ኦክሰንፎርድ የተጻፈው ሃሜት ትዝ አለው፡፡ የኦክሰንፎርድ ቤተሰብ በጦርነት ምክንያት እህል መሸጥ
ባለመቻሉ ምክንያት ከርስታቸው የሚያገኙት ገቢ በመቆሙ ኪሳራ ላይ መውደቁን፣ ሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት የቀራቸውን ሀብት ይዘው በጣሊያንና በፈረንሳይ መኖር እንደጀመሩ፣ ነገር ግን ሎርድ ኦክሰንፎርድ አንድ የአሜሪካ
የባንክ ባለንብረት ቤተሰብ ልጅ በማግባታቸው የተንደላቀቀ ኑሮዋቸው እንዳልተቋረጠባቸው አንብቧል፡፡ ስለዚህ እኚህን አሜሪካዊ ሴት ለማታለል
ከመነሳቱ በፊት መጠንቀቅ እንዳለበት ተረዳ፤ ቢያንስ ለሚቀጥሉት የበረራ ሰዓቶች፡፡
ለእኚህ ሴት መልካም ባህሪ ማሳየት እንዳለበት አውቋል፡ መቼም
ወይዘሮዋ ከመልከ መልካም ወጣት የሚጎርፍላቸውን የሙገሳ ቃላት የሚጠሉ አይመስሉም፡፡ አንገታቸው ላይ የተንጠለጠለውን ውድ የአንገት ጌጥ ጠጋ ብሎ አየው፡፡ እውነተኛ ጌጥ ነው፡፡ የፈረንሳይ አገር ስሪት ሲሆን
በ1880 ዓ.ም የተሰራ መሆኑን ገመተ፡፡
‹‹የአንገት ጌጥዎ የተሰራው በኦስካር ሚኒን አይደለም?›› ሲል
ጠየቃቸው እመቤቲቱን፡
‹‹ልክ ብለሃል››
‹‹በጣም ግሩም ጌጥ ነው››
‹‹አመሰግናለሁ፡፡››
እመቤት ኦክሰንፎርድ ቆንጆ ናቸው፡ ሎርድ ኦክሰንፎርድ ለምን
እንዳገቧቸው አወቀ፡፡ ነገር ግን ሴትየዋ ለምን እሳቸውን እንዳገቧቸው ሊገባው አልቻለም፤ ምናልባትም ከሃያ ዓመት በፊት ሰውየው የሴትየዋን ልብ መስረቅ ችለው ይሆናል፡
‹‹ፊላደልፊያ ውስጥ
የማውቃቸው መሰለኝ፤ የኔ ቤተሰቦች ስታንፎርድ ኮኔክቲከት ውስጥ ነው የሚኖሩትን የቫንዴርፖስት ቤተሰብን
የሚኖሩት›› አሉት እመቤት ኦክሰንፎርድ
‹‹በውነት!›› አለ ሄሪ የተደነቀ ይመስል፡፡ አሁንም ስለፊላደልፊያ ነው የሚያስበው ቅድም አገሬ ፊላደልፊያ ነው ወይስ ፔንሲልቫኒያ ነው ያለው? ጠፋበት፡፡ ወይ የተለያየ ስም ያለው አንድ ዓይነት ቦታ ይሁን ወይም አይሁን የሚያውቀው ነገር የለም፡፡
ትንሹ ልጅ ‹‹እኔ ፔርሲ እባላለሁ›› አለው፡፡
‹‹እኔ ሄሪ እባላለሁ›› አለው ሄሪም፡፡ ፔርሲ የራሱ የማዕረግ ስም
አለው የባላባት ዘር ስለሆነ፡፡ ይህን የማዕረግ ስም አባቱ እስኪሞት ይዞ
ይቆይና ከአባቱ ሞት በኋላ ሎርድ› የተባለውን የማዕረግ ስም ይወርሳል፡፡እነዚህ ሰዎች በማዕረግ ስማቸው ይኮራሉ፡፡ ፔርሲ ግን ለየት ይላል፡ በማዕረግ ስሙ መጠራት እንደማይፈልግ ለሄሪ ነግሮታል፡
ሄሪ ተቀመጠ፡፡ ማርጋሬት አጠገቡ ስለተቀመጠች ሌሎች ሳይሰሙ
ሊያናግራት እንደሚችል ተረድቷል፡፡ አይሮፕላኑ ጸጥ ረጭ ብሏል፡፡ ሁሉም ሰው በአግራሞት አይሮፕላኑን ይቃኛል፡፡
ሄሪ ዘና ለማለት ሞከረ፡፡ ጉዞው ውጥረት የበዛበት ሊሆን እንደሚችል አውቋል፡ ማርጋሬት እውነተኛ ማንነቱን ስላወቀች መጠነኛ ችግር ይገጥመው ይሆናል፡፡ ያቀረበላትን ሃሳብ የተቀበለች ቢሆንም ሀሳቧን
ልትለውጥ ወይም አፏ ሊያመልጣት ይችላል አምርረው ካልጠየቁት የአሜሪካን አገርን ኬላ ማለፍ አያቅተውም፡: ነገር ግን አሜሪካዊነቱን
ከተጠራጠሩትና አጥብቀው ከመረመሩት በሃሰት ፓስፖርት እንደሚሄድ
ያውቁበትና አለቀለት ማለት ነው፡
አንድ ሌላ ተሳፋሪ ሄሪ ፊት ለፊት ያለው መቀመጫ ላይ ተቀመጠ፡፡
ሰውየው ረጅም ሲሆን ራሱ ላይ ኮፍያ ደፍቷል። የለበሰው ሱፍ ልብስ
በጊዜው አሪፍ ልብስ ነበር፡ አሁን ግን ጊዜው አልፎበታል ጫማው ያረጀ
ሲሆን ክራቫቱ ካንገቱ ላይ ሳይወርድ አስር ዓመት የሞላው ይመስላል፡
ሰውየው ፖሊስ ይመስላል - ነጭ ለባሽ ፖሊስ፡፡
ሄሪ ከአይሮፕላኑ ወጥቶ መሄድ እንደሚችል ያውቃል፤ ማንም ተው
ሊለው አይችልም፤ ከአይሮፕላኑ መውጣት ከዚያም መጥፋት፡፡
ነገር ግን ለጉዞው የከፈለው 90 ፓውንድ አሳዘነው፡ ከዚያም በላይ ሌላ
የጉዞ ተራ ለማግኘት ሳምንታት ሊጠብቅ ይችላል፡፡ በዚያ መሃል ቢያዝስ!?
ሌላ ሃሳብ መጣለት፤ እንግሊዝ አገር እየተሽሎከለከ መኖር፡፡ ወዲያው ይህን ሀሳብ ከአዕምሮው አወጣው፡፡ በጦርነት ወቅት አገር ላገር መንከራተት ደግ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም የውጭ አገር ሰላይ ካለ ብሎ ሲያማትር ይውላል፡፡ ከዚያም በላይ ደግሞ የስደተኛ ኑሮ ቀላል አይደለም፡፡ በየቀኑ
የተለያየ ሆቴል ማደር፤ ፖሊስ ሲመጣ መደበቅና ሁልጊዜ መንከራተት፡
ፊት ለፊት የተቀመጠው ሰው ፖሊስ ቢሆንም እሱን ሊፈልግ እንዳልመጣ አውቋል፡ ምክንያቱም ሰውየው ተመቻችቶ ተቀምጦ ጉዞውን
ይጠብቃል፡ ለጊዜው የጎን ውጋት የሆነችበት ማርጋሬት ናት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በኬንፎሌት
፡
፡
#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ
ሄሪ ፍርድ ቤቱ የጣለበትን የዋስ ክፍያ ሳያስይዝ፣ በሃሰት ፓስፖርትና
ስም ተጠቅሞ አሜሪካዊ ነኝ እያለ እንዳልመጣ አሁን ሌባ መሆኑን የምታውቅ ልክ በስሙ ስትጠራው አመዱ ቡን አለ፡፡
ካገር ያሰደደው አስከፊ ነገር ሁሉ ዓይኑ ላይ ድቅን አለበት፡ የፍርድ ቤቱ እሰጥ አገባ፣ እስር ቤት የቆየባቸው ቀናትና የግዴታ ውትድርና
አገልግሎት፡
በኋላ ግን ዕድለኛነቱ ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡
ሄሪ ልጅቷ ግራ እንደገባት አየ፡፡ ስሟን ለስታወስ ሞከረና መጣለት
እመቤት ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ፡
ልጅቷ በመገረም አፈጠጠችበት።
‹‹ስሜ ሄሪ ቫንዴርፖስት ነው›› አላት፤ ካንቺ ይልቅ እኔ የተሻለ አስታውሳለሁ፡ አንቺ ማርጋሬት ኦክሰንፎርድ አይደለሽም? እንዴነት ነሽ?››
‹‹ደህና ነኝ›› አለች በድንጋጤ ደንዝዛ
ለሰላምታ እጁን ሲዘረጋላት ልትጨብጠው እጇን ስትሰድ መጨበጡን
ትቶ ‹‹ከዚህ በፊት ፖሊስ ጣቢያ እንዳላየሽኝ ሁኚ፧ እኔም እንዲሁ አደርጋለሁ›› አላት፡፡
ግራ መጋባቷ ሲለቃት ፈገግ አለች፡፡ የነገራት ገባትና ‹‹እንዴ ምን ነካኝ
ሄሪ ቫንዴርፖስት›› አለች፡
ሄሪ አሁን ቀለል አለው፡፡ በዓለም ላይ መቼም እንደኔ እድለኛ የለም አለ በሆዱ፡፡
ማርጋሬትም ‹የሆኖ ሆኖ የት ነበር የምንተዋወቀው?›› ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አንድ ዳንስ ቤት የተገናኘን ይመስለኛል›› አላት፡፡
‹‹ልክ ነው እዚያ ነው የማውቅህ›› አለች
በዚህ ጊዜ ፈገግ አለ፡፡
የሴራው ተካፋይ አደረጋት፡፡
በመቀጠልም ‹‹ቤተሰቦቼን ላስተዋውቅህ›› አለችና ‹‹እማማ አባባ ሚስተር ቫንዴርፖስትን ተዋወቁት ከ. . . ስትል ከአፏ ነጥቆ ‹‹ከአሜሪካ
ፔንሲልቫኒያ›› አለና ንግግሯን ጨረሰላት፡፡
ፔንሲልቫንያ የሚለው ቃል ካፉ ሲወጣ ዕድሉን ረገመ፡፡ ፔንሲልቫኒያ የት እንደሚገኝ አያውቅም፡፡
‹‹ይቺ እናቴ ናት፤ ይሄ አባቴ፤ ይሄ ደግሞ ወንድሜ ነው›› በማለት በማዕረግ ስማቸው አስተዋወቀችው:: ሄሪ ሁሉንም በዝና ያውቃቸዋል፡ ሄሪ የማርጋሬትን ቤተሰቦች ልባዊ በሆነ በአሜሪካውያን ተግባቢነት ባህሪ ሰላምታ
ሰጣቸው፡፡
ሎርድ ኦክሰንፎርድ እንደልማዳቸው በትዕቢት ተጀንነው ተኮፍሰዋል:
ሄሪ እናቷን ማነጋገር መረጠና ‹‹እንደም ነዎት የኔ፧ እመቤት? የተሰማራሁት
በእንቁ ጌጣጌጥ ንግድ ላይ ነው፤ እርስዎም በዓለም ላይ አለ የሚባል የዕንቁ ስብስብ እንዳለዎት ሰምቻለሁ›› አላቸው፡፡
‹‹እውነት ነው፤ ዕንቁ እወዳለሁ›› አሉት፡፡
ሄሪ የእመቤት ኦክሰንፎርድን የአሜሪካውያን የአነጋገር ቅላጼ ሲሰማ ቀልቡ ተገፈፈ፡፡ ስለእኚህ እመቤት መጽሔት ላይ አንብቧል፡፡ሴትየዋ እንግሊዛዊት ይመስሉት ነበር፡፡ መጽሔቶች ላይ ስለ ኦክሰንፎርድ የተጻፈው ሃሜት ትዝ አለው፡፡ የኦክሰንፎርድ ቤተሰብ በጦርነት ምክንያት እህል መሸጥ
ባለመቻሉ ምክንያት ከርስታቸው የሚያገኙት ገቢ በመቆሙ ኪሳራ ላይ መውደቁን፣ ሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት የቀራቸውን ሀብት ይዘው በጣሊያንና በፈረንሳይ መኖር እንደጀመሩ፣ ነገር ግን ሎርድ ኦክሰንፎርድ አንድ የአሜሪካ
የባንክ ባለንብረት ቤተሰብ ልጅ በማግባታቸው የተንደላቀቀ ኑሮዋቸው እንዳልተቋረጠባቸው አንብቧል፡፡ ስለዚህ እኚህን አሜሪካዊ ሴት ለማታለል
ከመነሳቱ በፊት መጠንቀቅ እንዳለበት ተረዳ፤ ቢያንስ ለሚቀጥሉት የበረራ ሰዓቶች፡፡
ለእኚህ ሴት መልካም ባህሪ ማሳየት እንዳለበት አውቋል፡ መቼም
ወይዘሮዋ ከመልከ መልካም ወጣት የሚጎርፍላቸውን የሙገሳ ቃላት የሚጠሉ አይመስሉም፡፡ አንገታቸው ላይ የተንጠለጠለውን ውድ የአንገት ጌጥ ጠጋ ብሎ አየው፡፡ እውነተኛ ጌጥ ነው፡፡ የፈረንሳይ አገር ስሪት ሲሆን
በ1880 ዓ.ም የተሰራ መሆኑን ገመተ፡፡
‹‹የአንገት ጌጥዎ የተሰራው በኦስካር ሚኒን አይደለም?›› ሲል
ጠየቃቸው እመቤቲቱን፡
‹‹ልክ ብለሃል››
‹‹በጣም ግሩም ጌጥ ነው››
‹‹አመሰግናለሁ፡፡››
እመቤት ኦክሰንፎርድ ቆንጆ ናቸው፡ ሎርድ ኦክሰንፎርድ ለምን
እንዳገቧቸው አወቀ፡፡ ነገር ግን ሴትየዋ ለምን እሳቸውን እንዳገቧቸው ሊገባው አልቻለም፤ ምናልባትም ከሃያ ዓመት በፊት ሰውየው የሴትየዋን ልብ መስረቅ ችለው ይሆናል፡
‹‹ፊላደልፊያ ውስጥ
የማውቃቸው መሰለኝ፤ የኔ ቤተሰቦች ስታንፎርድ ኮኔክቲከት ውስጥ ነው የሚኖሩትን የቫንዴርፖስት ቤተሰብን
የሚኖሩት›› አሉት እመቤት ኦክሰንፎርድ
‹‹በውነት!›› አለ ሄሪ የተደነቀ ይመስል፡፡ አሁንም ስለፊላደልፊያ ነው የሚያስበው ቅድም አገሬ ፊላደልፊያ ነው ወይስ ፔንሲልቫኒያ ነው ያለው? ጠፋበት፡፡ ወይ የተለያየ ስም ያለው አንድ ዓይነት ቦታ ይሁን ወይም አይሁን የሚያውቀው ነገር የለም፡፡
ትንሹ ልጅ ‹‹እኔ ፔርሲ እባላለሁ›› አለው፡፡
‹‹እኔ ሄሪ እባላለሁ›› አለው ሄሪም፡፡ ፔርሲ የራሱ የማዕረግ ስም
አለው የባላባት ዘር ስለሆነ፡፡ ይህን የማዕረግ ስም አባቱ እስኪሞት ይዞ
ይቆይና ከአባቱ ሞት በኋላ ሎርድ› የተባለውን የማዕረግ ስም ይወርሳል፡፡እነዚህ ሰዎች በማዕረግ ስማቸው ይኮራሉ፡፡ ፔርሲ ግን ለየት ይላል፡ በማዕረግ ስሙ መጠራት እንደማይፈልግ ለሄሪ ነግሮታል፡
ሄሪ ተቀመጠ፡፡ ማርጋሬት አጠገቡ ስለተቀመጠች ሌሎች ሳይሰሙ
ሊያናግራት እንደሚችል ተረድቷል፡፡ አይሮፕላኑ ጸጥ ረጭ ብሏል፡፡ ሁሉም ሰው በአግራሞት አይሮፕላኑን ይቃኛል፡፡
ሄሪ ዘና ለማለት ሞከረ፡፡ ጉዞው ውጥረት የበዛበት ሊሆን እንደሚችል አውቋል፡ ማርጋሬት እውነተኛ ማንነቱን ስላወቀች መጠነኛ ችግር ይገጥመው ይሆናል፡፡ ያቀረበላትን ሃሳብ የተቀበለች ቢሆንም ሀሳቧን
ልትለውጥ ወይም አፏ ሊያመልጣት ይችላል አምርረው ካልጠየቁት የአሜሪካን አገርን ኬላ ማለፍ አያቅተውም፡: ነገር ግን አሜሪካዊነቱን
ከተጠራጠሩትና አጥብቀው ከመረመሩት በሃሰት ፓስፖርት እንደሚሄድ
ያውቁበትና አለቀለት ማለት ነው፡
አንድ ሌላ ተሳፋሪ ሄሪ ፊት ለፊት ያለው መቀመጫ ላይ ተቀመጠ፡፡
ሰውየው ረጅም ሲሆን ራሱ ላይ ኮፍያ ደፍቷል። የለበሰው ሱፍ ልብስ
በጊዜው አሪፍ ልብስ ነበር፡ አሁን ግን ጊዜው አልፎበታል ጫማው ያረጀ
ሲሆን ክራቫቱ ካንገቱ ላይ ሳይወርድ አስር ዓመት የሞላው ይመስላል፡
ሰውየው ፖሊስ ይመስላል - ነጭ ለባሽ ፖሊስ፡፡
ሄሪ ከአይሮፕላኑ ወጥቶ መሄድ እንደሚችል ያውቃል፤ ማንም ተው
ሊለው አይችልም፤ ከአይሮፕላኑ መውጣት ከዚያም መጥፋት፡፡
ነገር ግን ለጉዞው የከፈለው 90 ፓውንድ አሳዘነው፡ ከዚያም በላይ ሌላ
የጉዞ ተራ ለማግኘት ሳምንታት ሊጠብቅ ይችላል፡፡ በዚያ መሃል ቢያዝስ!?
ሌላ ሃሳብ መጣለት፤ እንግሊዝ አገር እየተሽሎከለከ መኖር፡፡ ወዲያው ይህን ሀሳብ ከአዕምሮው አወጣው፡፡ በጦርነት ወቅት አገር ላገር መንከራተት ደግ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም የውጭ አገር ሰላይ ካለ ብሎ ሲያማትር ይውላል፡፡ ከዚያም በላይ ደግሞ የስደተኛ ኑሮ ቀላል አይደለም፡፡ በየቀኑ
የተለያየ ሆቴል ማደር፤ ፖሊስ ሲመጣ መደበቅና ሁልጊዜ መንከራተት፡
ፊት ለፊት የተቀመጠው ሰው ፖሊስ ቢሆንም እሱን ሊፈልግ እንዳልመጣ አውቋል፡ ምክንያቱም ሰውየው ተመቻችቶ ተቀምጦ ጉዞውን
ይጠብቃል፡ ለጊዜው የጎን ውጋት የሆነችበት ማርጋሬት ናት፡፡
#ከቡስካ_በስተጀርባ
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ሆራ ጥሩ ጥሩ የባራዝ አርጩሜ ይዞ እሱና ጎይቲ በሚዞሩበት መንደር ሲጓዙ በየምክንያቱ ጎይቲ አንተነህን በአርጩሜ
ይገርፋታል” ለሽንት ስትቆም ለምን ቆምሽ፣ እንቅፋት ሲመታት ለምን መታሽ፣ ደክሟት ቁጭ ስትል ለምን ቁጭ አልሽ እያለ
በየምክንያቱ እንዲገርፍ ባህሉ ያስገድዳል" ሴት ልጅ በኋላ ከቁጥጥር ውጭ ሆና እንዳታስቸግር፣ ባሏ እየገረፈ በማሽቆጥቆጥ ቅን ታዛዥ ሽር ያለች አገልጋይ እንድትሆን ያደርጋል"
ካርለት አልፈርድ ማስታወሻ፣ ካሜራ፣ ድንኳኗን በጨርቅ
ከረጢት ይዛ፣ የፍየል ቆዳዋን በመልበስ አብራቸው እየተጓዘች ከሎ
ጎይቲ የሚያደርጉትን ትቃኛለች የከሎ ዘመዶች ለከሎ የሚያደርጉለትን ስጦታም ትመለከታለች"
ከሎ ሆራ እናቱ ዘንድ ስጦታ ለመቀበል ላላ መንደር ሲሄድ፣ ካርለት እጅግ በጣም አዘነች" ከሎም በጣም ተሰማው። እናትዬዋ
እንዳዩት አቅፈው፣ አንገቱን ሲያሻሹ ቆዩና ካርለትና ሚስቱን ሰላም ብለው ትክዝ ብለው ቁጭ አሉ" ለልጃቸው ምን እንደሚያደርጉለት ጨነቃቸው። ለሱ ስጦታ ያዘጋጁለት መካከለኛ መጠን ያለው ሁለት
ቅል ቅቤና አንድ ቅል ማር ብቻ ነው ከሎ የእናቱን ሁኔታ አይቶ ኃዘን ተሰምቶት ዘወር ሲል፣ ካርለት ተጠጋቻቸው"
«ለምን ያለቅሳሉ?» አለች ትንሽ ዐረፍ ካለች በኋላ።
«ይእ! ልጄ የሚያስፈልገውን ያህል ስጦታ አላገኘማ።»
«እርስዎ ለልጅዎ የሚሰጡት ከብት፣ ፍየል... የለዎትም?»
«የለኝም»
«ለምን?»
«ይእ! እኔ ከብት፣ ፍየል... ኖሮኝም አያውቅም ወደፊትም አይኖረኝም" በልጃገረድነቴ ከብቶች፣ ፍየሎች፣ በጎች የአባቴ
ነበሩ" ባል ሳገባ ደግሞ፣ የባሌ ነበሩ። አሁን ባሌ ሞቷል፤ የከሎ አባት ቢኖር ለልጄ ብዙ ሀብት ይሰጠው ነበር።»
«የባልዎትን ሀብት አልወረሱም?
ይእ! ሚስት እንዴት የባሏን ሀብት ትወርሳለች? ባሏ ሲሞት ለወንድሙ በውርስ ትተላለፍና ወንድሙ ሌላውን ሀብት እንደ ወረሰ
እሷንም ይወርሳል። እኔም፣ ለባሌ ታናሽ ወንድም እያገለገልኩ እኖራለሁ"» አሁንም ባልቴቷ ፍዝዝ እንዳሉ ናቸው"
«ባልዎ የሞቱ ጊዜ መቼም እንዳሁኑ የበለተቱ አይመስለኝም፤ከታናሽ ወንድምየው ጋር ይቃበጡ ነበር?»
«ይ..እ ይሄማ ይጠየቃል፤ ባሌ እያለም ቢሆን ከታናሽ
ወንድምየው ጋር እንጨዋወታለን። እንዲያውም ከሎን የወለድኩት ከሆራ ሼላ ታናሽ ወንድም ነው።» ባልቴቷ ፈርጠም አሉ፣ የሞጨሞጨውን አይናቸውን ወደ ካርለት እየመለሱ።
«ምን? ማለቴ የከሎ ወላጅ አባት ሆራ ሼላ አይደለም ነው የሚሉኝ? የሚጠራው እኮ ከሎ ሆራ ተብሎ ነው።» ካርለት መልሱን ለመስማት ጓጓች።
«ይ..እ! በኛ ባህል አንድ ሴት ከባሏ ታናሽ ወንድም ልጅ ብትወልድ የልጇ አባት የሚሆነው ባሏ ነው። ባሏ እንኳ ሞቶ ከሌላ ወንድ ብትወልድ የልጇ አባት ስም በሟቹ ባሏ ስም ነው
ሚሆነው;»
«እና የከሎ እውነተኛ ወላጅ አባት በሕይወት አለ?»
«አዎን አለ።»
«አሁን እርስዎን የሚጦርዎ ማነው? »
«እሱና ልጆቼ።» ካርለት ይህ ለሷ እስከ አሁን ያልሰማችው አዲስ ነገር ነው" ከሎ ሆራም ስለ ወላጅ አባቱ የሚያውቅ አልመሰላትም" ምክንያቱም የግል ታሪኩን ሲነግራት አባቴ ሞቷል ብሎ ነበር።
ካርለት ወደ ከሎ ሄዳ ጉዳዩን ስትነግረው በጣም ተገረመ። ይህን ምሥጢር እሱ ቀደም ብሎ አያውቅም። ወደፊትም ለማወቅ የሚችል
አልመሰለውም።
«ካርለት አሁን የምትነግሪኝ ሁሉ ለኔ አዲስ ነገር ነውኮ፤
በጥረትሽ ወላጅ አባቴን እንዳውቅና እንዳገኝ እያደረግሽኝ እኮ ነው»
አላት ከሎ።
ካርለት፣ «ምንም አይደለም፣ ይልቁንስ አባትክን ማግኘ;
ይኖርብናል» አለችው።
።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።
ጂሚ ሼላ ብዙ አላረጀም። ሰውነቱ ስላለው ጠንካራ ቢሆንም ዕድሜውን ከ60 በላይ ነው። ካርለትና ከሎ ሆራ እሱ ዘንድ ሲመጡ ከጎጆው ፊት ለፊት በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ፀሐይ እየሞቀ አገኙት። ካርለት ጂሚን ስታየው ደንገጥ ብላ ከሎን ዞራ አየችው ከሎ ሆራና ጂሚ ሼላ በጣም ይመሳሰላሉ። ካርለት ጂሚን እንዳየች
ከሎ ሆራ አርጅቶ ከፊት ለፊት የተቀመጠ መስሏት ነበር"
ጂሚ ሼላ ከሎ ሆራን ለመጠየቅ ሻንቆ መንደር ሄዶ ሳለ ካርለትን
አይቷታል። ስለዚህ እንዳያቸው አወቃቸው" እነሱም ሄደው አጠገቡ
ቁጭ አሉና በሐመር ባህል መሠረት ዕረፍት ከወሰዱ በኋላ፣
«እንዴት ነዎት?» አሉት።
«ደህና ነኝ" እናንተስ እንዴት ናችሁ?» አለ ጂሚ ሼላ።
«ከሎ ለእርስዎ ምንዎ ነው?»
«የወንድሜ ልጅ ነው"» ጂሚ ካርለትን በተመስጦ
ተመለከታት።
«መልኩ ግን ቁርጥ እርስዎን ነው የሚመስለው?»
«ሆራ ሼላና እኔም እንመሳሰል ነበር እኮ።»
«ከሎ የእርስዎ ልጅ እንደሆነ ሰምቻለሁ" እንዴት ነው?»
ካርለት ዋናው ነጥብ ላይ ዘላ ጥቡልቅ አለች።
«እንዴት ተደርጎ?» ጂሚ ሼላ መልሶ ጠየቃት"
«እርስዎ ከከሎ እናት ጋር... ያረጉ አልነበረም? »
«ያማ ባህል ነው።»
«እና እንዴት ከሎ የማን ልጅ እንደሆነ ያጡታል?»
«ይሕ! በሐመር ባህል ልጅ ከወንድም ተወለደም፣ ከውሽማ በአባትነት የሚታወቀው ባል ነው። እኔም ከከሎ እናት ጋር ወንድሜ እያለም ሆነ፣ ከዚያን ወዲህ ግንኙነት ቢኖረኝም ከሎ ከማንኛችን
እንደ ተወለደ የምታውቀው እናቱ ብቻ ናት"»
ካርለት ነገሩ ገባት። «በሐመር ማኅበረሰብ የልጇን ትክክለኛ ወላጅ አባት የምታውቀው እናት ብቻ ናት ለካ!» ብላ፣ ተደንቃ
ቆየችና፣ «ለምን ስምዎ ጂሚ ተባለ?» አለችው፣ ጂሚ ሼላን።
«አንድ ጂሚ የሚባል ፈረንጅ እዚህ መጥቶ፣ ከአባቴ ጋር ተዋውቆ ነበር። እንዳጋጣሚ እናቴ እሱ ከዚህ ሳይሄድ እኔን ወለደችኝ በሐመር ባህል እንግዳ መጥቶ በአጋጣሚ ልጅ ቢወለድ ስሙ
በዚያው ሰው ስም ነው የሚጠራው።»
ካርለት ነገሩ ወዲያው ገባት" ምክንያቱም በዚህ መልክ በሷ ስም የሚጠሩ ሁለት ሕፃናት ታውቃለች
«የከሎ ሆራ እናት፣ የከሎን ትክክለኛ አባት ጠይቄያቸው እርስዎ እንደሆኑ ነገሩኝ» ስትለው፣ ጂሚ ምንም መልስ ሳይሰጣት ከሎ
ሆራን ዓይን ዓይኑን ሲያይ ቆየና እጁን ጎተት አድርጎ ያዘው" ከሎ የወላጅ አባቱ ጣቶች እጁን ሲነኩት፣ ደስታ አይሉት ኃዘን ቅጡ የጠፋ ስሜት በመላ አካሉ ተስለከለከበት" ትንሽ ቆይተው አባትና
ልጅ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ተቃቀፉ። የወላጅና ልጅ ፍቅር
በመካከላቸው ታየ ካርለትም የደስታ እንባ አነባች የሐመር ፀሐይ
ግን ወደ መሠወሪያዋ ወደቀች"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሎ ሆራ በፈቃድ ከዩኒቨርሲቲው በተገለለ በሁለተኛ ዓመቱ
ትምህርቱን ለማጠናቀቅ አዲስ አበባ ሄደ። ከሎ አዲሳባ ዩኒቨርሲቲ
ገብቶ ትምህርቱን ከጀመረ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ለስቲቭ ደወለለት። ቀጠሮ ተሰጣጡና እሑድ ዕለት ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ከሎ
ከስቲቭ ቀድሞ በቀጠሮው ቦታ ተገኘ። ስቲቭ ልክ በሰዓቱ ሲገባ፣ከሎ ገና ከበሩ ወደ ቀኝ ሲታጠፍ ተመለከተው። ስቲቭ፣ የሆነ ፖስታ ይዞ የመሮጥ ያህል ሲራመድ፣ ከሆቴሉ ማዕዘን ላይ ካለው ሶፋ ላይ ነጫጭ ጥርሶቹን የሚያብለጨልጨውን ከሎን ተመለከተው። ስቲቭ
በማስብበት ወቅት ላገኝህ በመቻሌ በጣም ተደስቻለሁ» አለ ስቲቭ፣
የፈገግታውን መጠን እየጨመረ።
#ድንግል_ውበት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ከሎ ሆራ ጥሩ ጥሩ የባራዝ አርጩሜ ይዞ እሱና ጎይቲ በሚዞሩበት መንደር ሲጓዙ በየምክንያቱ ጎይቲ አንተነህን በአርጩሜ
ይገርፋታል” ለሽንት ስትቆም ለምን ቆምሽ፣ እንቅፋት ሲመታት ለምን መታሽ፣ ደክሟት ቁጭ ስትል ለምን ቁጭ አልሽ እያለ
በየምክንያቱ እንዲገርፍ ባህሉ ያስገድዳል" ሴት ልጅ በኋላ ከቁጥጥር ውጭ ሆና እንዳታስቸግር፣ ባሏ እየገረፈ በማሽቆጥቆጥ ቅን ታዛዥ ሽር ያለች አገልጋይ እንድትሆን ያደርጋል"
ካርለት አልፈርድ ማስታወሻ፣ ካሜራ፣ ድንኳኗን በጨርቅ
ከረጢት ይዛ፣ የፍየል ቆዳዋን በመልበስ አብራቸው እየተጓዘች ከሎ
ጎይቲ የሚያደርጉትን ትቃኛለች የከሎ ዘመዶች ለከሎ የሚያደርጉለትን ስጦታም ትመለከታለች"
ከሎ ሆራ እናቱ ዘንድ ስጦታ ለመቀበል ላላ መንደር ሲሄድ፣ ካርለት እጅግ በጣም አዘነች" ከሎም በጣም ተሰማው። እናትዬዋ
እንዳዩት አቅፈው፣ አንገቱን ሲያሻሹ ቆዩና ካርለትና ሚስቱን ሰላም ብለው ትክዝ ብለው ቁጭ አሉ" ለልጃቸው ምን እንደሚያደርጉለት ጨነቃቸው። ለሱ ስጦታ ያዘጋጁለት መካከለኛ መጠን ያለው ሁለት
ቅል ቅቤና አንድ ቅል ማር ብቻ ነው ከሎ የእናቱን ሁኔታ አይቶ ኃዘን ተሰምቶት ዘወር ሲል፣ ካርለት ተጠጋቻቸው"
«ለምን ያለቅሳሉ?» አለች ትንሽ ዐረፍ ካለች በኋላ።
«ይእ! ልጄ የሚያስፈልገውን ያህል ስጦታ አላገኘማ።»
«እርስዎ ለልጅዎ የሚሰጡት ከብት፣ ፍየል... የለዎትም?»
«የለኝም»
«ለምን?»
«ይእ! እኔ ከብት፣ ፍየል... ኖሮኝም አያውቅም ወደፊትም አይኖረኝም" በልጃገረድነቴ ከብቶች፣ ፍየሎች፣ በጎች የአባቴ
ነበሩ" ባል ሳገባ ደግሞ፣ የባሌ ነበሩ። አሁን ባሌ ሞቷል፤ የከሎ አባት ቢኖር ለልጄ ብዙ ሀብት ይሰጠው ነበር።»
«የባልዎትን ሀብት አልወረሱም?
ይእ! ሚስት እንዴት የባሏን ሀብት ትወርሳለች? ባሏ ሲሞት ለወንድሙ በውርስ ትተላለፍና ወንድሙ ሌላውን ሀብት እንደ ወረሰ
እሷንም ይወርሳል። እኔም፣ ለባሌ ታናሽ ወንድም እያገለገልኩ እኖራለሁ"» አሁንም ባልቴቷ ፍዝዝ እንዳሉ ናቸው"
«ባልዎ የሞቱ ጊዜ መቼም እንዳሁኑ የበለተቱ አይመስለኝም፤ከታናሽ ወንድምየው ጋር ይቃበጡ ነበር?»
«ይ..እ ይሄማ ይጠየቃል፤ ባሌ እያለም ቢሆን ከታናሽ
ወንድምየው ጋር እንጨዋወታለን። እንዲያውም ከሎን የወለድኩት ከሆራ ሼላ ታናሽ ወንድም ነው።» ባልቴቷ ፈርጠም አሉ፣ የሞጨሞጨውን አይናቸውን ወደ ካርለት እየመለሱ።
«ምን? ማለቴ የከሎ ወላጅ አባት ሆራ ሼላ አይደለም ነው የሚሉኝ? የሚጠራው እኮ ከሎ ሆራ ተብሎ ነው።» ካርለት መልሱን ለመስማት ጓጓች።
«ይ..እ! በኛ ባህል አንድ ሴት ከባሏ ታናሽ ወንድም ልጅ ብትወልድ የልጇ አባት የሚሆነው ባሏ ነው። ባሏ እንኳ ሞቶ ከሌላ ወንድ ብትወልድ የልጇ አባት ስም በሟቹ ባሏ ስም ነው
ሚሆነው;»
«እና የከሎ እውነተኛ ወላጅ አባት በሕይወት አለ?»
«አዎን አለ።»
«አሁን እርስዎን የሚጦርዎ ማነው? »
«እሱና ልጆቼ።» ካርለት ይህ ለሷ እስከ አሁን ያልሰማችው አዲስ ነገር ነው" ከሎ ሆራም ስለ ወላጅ አባቱ የሚያውቅ አልመሰላትም" ምክንያቱም የግል ታሪኩን ሲነግራት አባቴ ሞቷል ብሎ ነበር።
ካርለት ወደ ከሎ ሄዳ ጉዳዩን ስትነግረው በጣም ተገረመ። ይህን ምሥጢር እሱ ቀደም ብሎ አያውቅም። ወደፊትም ለማወቅ የሚችል
አልመሰለውም።
«ካርለት አሁን የምትነግሪኝ ሁሉ ለኔ አዲስ ነገር ነውኮ፤
በጥረትሽ ወላጅ አባቴን እንዳውቅና እንዳገኝ እያደረግሽኝ እኮ ነው»
አላት ከሎ።
ካርለት፣ «ምንም አይደለም፣ ይልቁንስ አባትክን ማግኘ;
ይኖርብናል» አለችው።
።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።
ጂሚ ሼላ ብዙ አላረጀም። ሰውነቱ ስላለው ጠንካራ ቢሆንም ዕድሜውን ከ60 በላይ ነው። ካርለትና ከሎ ሆራ እሱ ዘንድ ሲመጡ ከጎጆው ፊት ለፊት በርኮታው ላይ ቁጭ ብሎ ፀሐይ እየሞቀ አገኙት። ካርለት ጂሚን ስታየው ደንገጥ ብላ ከሎን ዞራ አየችው ከሎ ሆራና ጂሚ ሼላ በጣም ይመሳሰላሉ። ካርለት ጂሚን እንዳየች
ከሎ ሆራ አርጅቶ ከፊት ለፊት የተቀመጠ መስሏት ነበር"
ጂሚ ሼላ ከሎ ሆራን ለመጠየቅ ሻንቆ መንደር ሄዶ ሳለ ካርለትን
አይቷታል። ስለዚህ እንዳያቸው አወቃቸው" እነሱም ሄደው አጠገቡ
ቁጭ አሉና በሐመር ባህል መሠረት ዕረፍት ከወሰዱ በኋላ፣
«እንዴት ነዎት?» አሉት።
«ደህና ነኝ" እናንተስ እንዴት ናችሁ?» አለ ጂሚ ሼላ።
«ከሎ ለእርስዎ ምንዎ ነው?»
«የወንድሜ ልጅ ነው"» ጂሚ ካርለትን በተመስጦ
ተመለከታት።
«መልኩ ግን ቁርጥ እርስዎን ነው የሚመስለው?»
«ሆራ ሼላና እኔም እንመሳሰል ነበር እኮ።»
«ከሎ የእርስዎ ልጅ እንደሆነ ሰምቻለሁ" እንዴት ነው?»
ካርለት ዋናው ነጥብ ላይ ዘላ ጥቡልቅ አለች።
«እንዴት ተደርጎ?» ጂሚ ሼላ መልሶ ጠየቃት"
«እርስዎ ከከሎ እናት ጋር... ያረጉ አልነበረም? »
«ያማ ባህል ነው።»
«እና እንዴት ከሎ የማን ልጅ እንደሆነ ያጡታል?»
«ይሕ! በሐመር ባህል ልጅ ከወንድም ተወለደም፣ ከውሽማ በአባትነት የሚታወቀው ባል ነው። እኔም ከከሎ እናት ጋር ወንድሜ እያለም ሆነ፣ ከዚያን ወዲህ ግንኙነት ቢኖረኝም ከሎ ከማንኛችን
እንደ ተወለደ የምታውቀው እናቱ ብቻ ናት"»
ካርለት ነገሩ ገባት። «በሐመር ማኅበረሰብ የልጇን ትክክለኛ ወላጅ አባት የምታውቀው እናት ብቻ ናት ለካ!» ብላ፣ ተደንቃ
ቆየችና፣ «ለምን ስምዎ ጂሚ ተባለ?» አለችው፣ ጂሚ ሼላን።
«አንድ ጂሚ የሚባል ፈረንጅ እዚህ መጥቶ፣ ከአባቴ ጋር ተዋውቆ ነበር። እንዳጋጣሚ እናቴ እሱ ከዚህ ሳይሄድ እኔን ወለደችኝ በሐመር ባህል እንግዳ መጥቶ በአጋጣሚ ልጅ ቢወለድ ስሙ
በዚያው ሰው ስም ነው የሚጠራው።»
ካርለት ነገሩ ወዲያው ገባት" ምክንያቱም በዚህ መልክ በሷ ስም የሚጠሩ ሁለት ሕፃናት ታውቃለች
«የከሎ ሆራ እናት፣ የከሎን ትክክለኛ አባት ጠይቄያቸው እርስዎ እንደሆኑ ነገሩኝ» ስትለው፣ ጂሚ ምንም መልስ ሳይሰጣት ከሎ
ሆራን ዓይን ዓይኑን ሲያይ ቆየና እጁን ጎተት አድርጎ ያዘው" ከሎ የወላጅ አባቱ ጣቶች እጁን ሲነኩት፣ ደስታ አይሉት ኃዘን ቅጡ የጠፋ ስሜት በመላ አካሉ ተስለከለከበት" ትንሽ ቆይተው አባትና
ልጅ ከመቀመጫቸው ብድግ ብለው ተቃቀፉ። የወላጅና ልጅ ፍቅር
በመካከላቸው ታየ ካርለትም የደስታ እንባ አነባች የሐመር ፀሐይ
ግን ወደ መሠወሪያዋ ወደቀች"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ከሎ ሆራ በፈቃድ ከዩኒቨርሲቲው በተገለለ በሁለተኛ ዓመቱ
ትምህርቱን ለማጠናቀቅ አዲስ አበባ ሄደ። ከሎ አዲሳባ ዩኒቨርሲቲ
ገብቶ ትምህርቱን ከጀመረ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ለስቲቭ ደወለለት። ቀጠሮ ተሰጣጡና እሑድ ዕለት ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ከሎ
ከስቲቭ ቀድሞ በቀጠሮው ቦታ ተገኘ። ስቲቭ ልክ በሰዓቱ ሲገባ፣ከሎ ገና ከበሩ ወደ ቀኝ ሲታጠፍ ተመለከተው። ስቲቭ፣ የሆነ ፖስታ ይዞ የመሮጥ ያህል ሲራመድ፣ ከሆቴሉ ማዕዘን ላይ ካለው ሶፋ ላይ ነጫጭ ጥርሶቹን የሚያብለጨልጨውን ከሎን ተመለከተው። ስቲቭ
በማስብበት ወቅት ላገኝህ በመቻሌ በጣም ተደስቻለሁ» አለ ስቲቭ፣
የፈገግታውን መጠን እየጨመረ።
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ትልቁ የሮማ ስታዲዬም በተመልካቾች ተጨናንቋል፡፡
መንገዶች ተጣበዋል
ለተሽከርካሪ ዝግ በሆነው መንገድ ላይ ህዝቡ
እንደ ጉንዳን ይርመሰመሳል፡ ሳቅ ጨዋታ, ዳንኪራ ሁሉም እንደየግል ዝንባሌው ያሻውን ይፈፅማል። ከዘመናዊው ስታዲዬም
በጣልያንኛ በእንግሊዝኛ• በፈረንሳይኛ… ስለውድድሩ ታላቅነት ስለ ውድድሩ አጀማመር ተወዳዳሪዎች ምርጥነት ስለ ያሸንፋሉ
ተብለው ስለሚገመቱ አትሌቶች በተለያየ ቋንቋ ይተነበያል።
አኜስ ሎካዬን ወደ ሮማ እንዲሄድና ውድድሩን እንዲያይ ያግባባቸው ከብዘ ልፋትና ድካም በኋላ ነው፡፡
“…ሉካዬ ውድድሩን ማዬት መቻል አለብን!” ስትለው:
"አኜስ አንች ሂጂ እኔ ግን እዚሁ መቆየት እፈልጋለሁ።
ምናልባት አንቺ ከተመለሽ በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ሄጄ ዘመዶቼን ብፈልግ ደስ ይለኛል"
“ሎካዬ አብረኸኝ እንድትሆን እፈልጋለሁ: ጣልያን ውስጥ ጥሩ የመዝናናት እድል ይኖረናል። ወንድሜና ሴት ጓደኛው አብረን እንድንሆን ይፈልጋሉ ልጃችንም ክሪናም ከሁለታችን ጋር መሆኑን
እንደምትመርጥ ነግራኛለች፡፡
“ሊሆን ይችላል አኜስ ከእነሱ ይልቅ አንች እኔን በሚገባ ታውቂኛለሽ፡ ሮማ በመሄድ ደስተኛ ይሆናል ብለሽ እንደማትገምች
ነው የማስበው፡ እዚህ ብሆን ግን ቢያንስ የልጅነት ጊዜዬን እያሰብኩ
በፀጥታው ልዝናና እችላለሁ: ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስም በመሄድ
በማዕበሉ ውሃ እግሮቼን እየነከርሁ ለመደሰት እሞክራለሁ: ሮም ሄጄ ግን ጎንና ጎኔ ጨዋታ ወዳድና ደስተኛ ሰዎች ይቀመጡና
እየጎነታተሉ እንድጫወት ተፅዕኖ ያደርጉብኛል፡፡ እየቆየ ግን ዝምታዬ እየከበዳቸው ሲመጣ ይሸሹኛል። ያኔ ጩኸቱ በሚያስበረግግ
ፀጥታ እዋጥና አዕምሮዬ ይረበሻል። ስለዚህ አኜስ! እባክሽን እኔን እንሂድ ማለትሽን ተይኝና ከሌሉች ጋር ሄደሽ ተዝናንተሽ ተመለሽ አላት ረጋ ብሎ
“ኦ አምላኬ! ለምን ይኸን ቅዠትህን አታቆምም። ስግብግብ አትሁን እሽ! ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል ኦለብህ፡ ግትርነትህንና
የገነተረ አስተሳሰብህን አለዝበው" አፈጠጠችበት፡፡
…ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል አለብህ አባባሏ ውስጡን ረበሸው፡ ሉካዩ ራሱን አይወድም ሌሎች ደስ ሲላቸው ማየት
ያረካዋል። እራሱን ግን ለማዝናናት እንዳይችል በልጅነቱ ከወላጆቹና
ከዘመዶቹ ካደገበት ቀዬ ነጥቀው በጭንቀት በሃዘን… እያለቀሰ!
ማንነታቸውን የማያውቃቸው ሰዎች እንደ
አውሬ ደስታውን
ገነጣጥለው በልተውበታል፡ ተስፋውን አምክነውበታል፧ ስሜቱን ጭምትርትር አድርገው አኮራምተውበታል፡፡ እድሜው እየጨመረ
በሄደ ቁጥር ከጠባሳው በታች ሊድን የማይችል የቁስሉ ጎሚ እየበረታበት መጣ። ራሱን ሊያክም ሞከረ ውስጡ ግን እያመረቀዘ በሰራ አካላቱ የስቃይ መርዙ ተሰራጨ፡
“አኜስ! ለምን ስቃዬን አትረጅልኝም ሁሌ ለሞን አሸናፊነት ትመርጫለሽ!"
“ሎካዬ! ተው እንዲህ ምርር አትበል ልለይህ አለመፈለጌ
ላንተ ካለማሰብ የመጣ ነው ብለህ ታስባለህ? እንደዚያማ ላለማሰብ
ሞክር" ብላ አንገቷን ሰበር ስታደርግ ሎካዬ ጠጋ ብሎ ፀጉሯን ደባበሰና፡-
“ይቅር በይኝ እሽ አብረን እንሄዳለን" ሲል ቀና ብላ
አይታው እንባዋ ከአይኖችዋ ረገፉ:: ሎካዬ ግን እንባዋን ማየቱ
ከብዶት ፀጉሯን ስሞ ወጣ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በተለያየ ቀለማት ያሸበረቁ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሜዳውን ሞልተው እክሮባት ሲያሳዩ እንደቆዩ እውቁ ጣሊያናዊ አቀንቃኝ
ከሙዚቃው ጋር አጣጥሞ ድምፁ ሲያስረቀርቀው በስቴዲየሙ ውስጥ
ያለው ህዝብ አድናቆቱን በጭብጨባ በፉጨት በጩኸት በጥሩንባ በከበሮ
ሲገልፅ ድምፃዊው አሳ እንደሚውጥ ትልቅ አሳ ፉን
ከፍቶ ሲዘፍን በስታዲየሙ ዙሪያ የተደገኑት ማጉያዎች ድምፁን አስተጋቡት:: አሁንም ጭብጨባ ጩኸት ደስታ ሁካታ ሆነ፤
ጭፈራው ቀለጠ፡ ርችት ተለኮሰ፡፡
ከዚያ ከያገሩ የመጡት ሯጮች ወደ መወዳደሪያው ቦታ ሲወጡ ተመልካቹ
ቆሞ በጭብጨባ
ተቀበላቸው፡፡ ከያገሩ
ስለተወከሉት ተወዳዳሪዎች ማንነት ጋዜጠኞች በየቋንቋው መዘርዘር
ቀጠሉ፡
አኜስ ሎካዬ ከሪናና የአኜስ ወንድም ከሴት ጓደኛው ጋር
ሮም ስታዲዬም ናቸው: ከሎካዬ በስተቀር ሁሉም ያጨበጭባሉ ብድግ ቁጭ ይላሉ ይለፈልፋሉ… ሎካዬ ግን በብዙ ሺ ህዝብ መሀል ሆኖ ያልማል የልጅነቱን ህይወት የወላጆቹን ቀዬ...
ተወዳዳሪዎች ተደረደሩ፤ ችቦው ተለኮሰ፤ ማራቶን የሮማ ማራቶን ተጀመረ፡
ከዚያ በስቴዲየሙ ውስጥ የጥቂት አትሌቶች ገድልና
በዛኔው ውድድርም ያሸንፉ ይሆናል የሚለው ግምት ተለፈፈ፡፡አውሮፓውያን አሜሪካውያን ሩቀ ምስራቆች የአሰለፏቸው
አትሌቶች መጠን በ ውድድር አፍሪካውያን ተወዳዳሪዎችም በተወሰኑ አትሌቶች መወከላቸው ተነገረ፡፡
ከክርስቶስ ልደት በፊት በአራት መቶ ዘጠና በፔርሽያና አቴና በተፈጠረው ድንገተኛ የጦር ወረራ ትንኮሳ የተደናገጡት
አቴናውያን ፊዲፒደስ የተባለውን ጀግና ስፖርት ላኩት: ፊዲፒደስም
ለሃምሳ ሰዓታት ካለ ምግብና መጠጥ ሩጦ መልዕክቱን አድርሶ
በመመለሱ ውጊያው ተጀመረ፡፡
የአምባገነኑ የፔርሺያ ኃይል
ግን የማታ ማታ ሟሾ የውጊያው ድል ፎክሮ ጦር አውድማ ከሄደው ከፔርሽያው መሪ
ከዳሪዮስ እጅ ወጥቶ አቴናውያን እጅ ገባ፡፡
የአቴና ፍቅር ያማለለው ጀግናው ሯጭና ተዋጊ
ፌዲፒደስም ያንን ያገሩን ታላቅ ድል ሲያይ ደስታ
ፈንቅሎት አቅጠበጠው ስለዚህ ያንን ታላቅ ድል ለወገኑ ለማብሰር ቂጤማ
የያዘች እርግቡን ህሊናው ቆጥ ላይ አስፍሮ ሀያ ሁለት ማይልስ ካለ እረፍት የተነሳውን ክቡር ቃል ሊያደርስ ሮጠ፡፡
ፊዲፒደስ ከተማ
ሲደርስ አካሉ ደክሞ ! ሕይወቱ የተንጠለጠለችው ጠንካራ ሞራሉ ላይ ነበርና ወገን ሊያገኝ ያን
እንደ አልማዝ የሚያንፀባርቅ ቃል እያከለከለከ “ቪክትሪ" ብሉ ቃሏን ብቻ አሰምቶ ህዝቡ ሲደሰት እሱ ግን ሕይወቱን ለአገሩ ድል ሰዋ እየሳቀ አንቀላፋ!
መልካም ሥራና እውነት
ግን ውሎ አድሮ ከትቢያ
መነሳታቸው የክብር ሥፍራቸውን መያዛቸው አይቀርምና በአስራ
ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ግሪኮች የፊዲፒደስን ውለታ ለመክፈልተ ተስማሙ፡፡ መልካሙ ስሙን ከመቃብር ውጭ ሊያውለበልቡት
አቀዱ! ስለዚህ ባምላካቸው መሪ በዜውስ ስም ሰይመው የኦለምፒክ
ማራቶን ጀመሩ… ያ የመልካም ስራ ሽቶ መዓዛም አለማችንን
አወዳት፡፡ ከዚያ የማራቶን ሩጫ ውድድር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንና በምዕራባውያን አገሮች በተለይ ሩጫን ዘመናዊ
ለማድረግ ሳይንሳዊ አሰለጣጠን ዘዴዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን አትሌቶች ከህፃንነታቸው ጀምሮ እየተመለመሉ ድንቅ
ተወዳዳሪዎችን ማፍራት መቻሉም ተናገረ፡፡
ሚዲያዎች ተወዳዳሪዎች የደረሱበትን ማን እየመራ
እንደሆነ ገለፁ፡፡የሚመራው አፍሪካዊ' ነው ሲባል ስለ ዘመናዊ የሩጫ አሰለጣጠን ዘዴ የሰማው ተመልካች ግራ የገባው መሰለ፡፡ብዙዎች ግን በማራቶን እሩጫ ትልቁ ዘዴ ትንፋሽን መጠበቅና ሃይልን እየቆጠቡ ቆይቶ የተወስነ ርቀት ሲቀር አፈትልኮ እንደ
ቀስት መወርወር ነው፡፡ ሲጀመር አካባቢ የቀደመ በስተመጨረሻ አትሌቶችን እየተሰናበተ ውራ ይወጣል' እየተባባሉ ተሳለቁ፡፡
ህዝቡን ከሚያዝናና ዝግጅቶች ጣልቃ ላይ የማራቶን ተወዳዳሪዎች ደረጃ እንደገና ተጠቀሰ:: አሁንም “አፍሪካዊው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ትልቁ የሮማ ስታዲዬም በተመልካቾች ተጨናንቋል፡፡
መንገዶች ተጣበዋል
ለተሽከርካሪ ዝግ በሆነው መንገድ ላይ ህዝቡ
እንደ ጉንዳን ይርመሰመሳል፡ ሳቅ ጨዋታ, ዳንኪራ ሁሉም እንደየግል ዝንባሌው ያሻውን ይፈፅማል። ከዘመናዊው ስታዲዬም
በጣልያንኛ በእንግሊዝኛ• በፈረንሳይኛ… ስለውድድሩ ታላቅነት ስለ ውድድሩ አጀማመር ተወዳዳሪዎች ምርጥነት ስለ ያሸንፋሉ
ተብለው ስለሚገመቱ አትሌቶች በተለያየ ቋንቋ ይተነበያል።
አኜስ ሎካዬን ወደ ሮማ እንዲሄድና ውድድሩን እንዲያይ ያግባባቸው ከብዘ ልፋትና ድካም በኋላ ነው፡፡
“…ሉካዬ ውድድሩን ማዬት መቻል አለብን!” ስትለው:
"አኜስ አንች ሂጂ እኔ ግን እዚሁ መቆየት እፈልጋለሁ።
ምናልባት አንቺ ከተመለሽ በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ሄጄ ዘመዶቼን ብፈልግ ደስ ይለኛል"
“ሎካዬ አብረኸኝ እንድትሆን እፈልጋለሁ: ጣልያን ውስጥ ጥሩ የመዝናናት እድል ይኖረናል። ወንድሜና ሴት ጓደኛው አብረን እንድንሆን ይፈልጋሉ ልጃችንም ክሪናም ከሁለታችን ጋር መሆኑን
እንደምትመርጥ ነግራኛለች፡፡
“ሊሆን ይችላል አኜስ ከእነሱ ይልቅ አንች እኔን በሚገባ ታውቂኛለሽ፡ ሮማ በመሄድ ደስተኛ ይሆናል ብለሽ እንደማትገምች
ነው የማስበው፡ እዚህ ብሆን ግን ቢያንስ የልጅነት ጊዜዬን እያሰብኩ
በፀጥታው ልዝናና እችላለሁ: ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስም በመሄድ
በማዕበሉ ውሃ እግሮቼን እየነከርሁ ለመደሰት እሞክራለሁ: ሮም ሄጄ ግን ጎንና ጎኔ ጨዋታ ወዳድና ደስተኛ ሰዎች ይቀመጡና
እየጎነታተሉ እንድጫወት ተፅዕኖ ያደርጉብኛል፡፡ እየቆየ ግን ዝምታዬ እየከበዳቸው ሲመጣ ይሸሹኛል። ያኔ ጩኸቱ በሚያስበረግግ
ፀጥታ እዋጥና አዕምሮዬ ይረበሻል። ስለዚህ አኜስ! እባክሽን እኔን እንሂድ ማለትሽን ተይኝና ከሌሉች ጋር ሄደሽ ተዝናንተሽ ተመለሽ አላት ረጋ ብሎ
“ኦ አምላኬ! ለምን ይኸን ቅዠትህን አታቆምም። ስግብግብ አትሁን እሽ! ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል ኦለብህ፡ ግትርነትህንና
የገነተረ አስተሳሰብህን አለዝበው" አፈጠጠችበት፡፡
…ለሌሎች ደስታ ማሰብ መቻል አለብህ አባባሏ ውስጡን ረበሸው፡ ሉካዩ ራሱን አይወድም ሌሎች ደስ ሲላቸው ማየት
ያረካዋል። እራሱን ግን ለማዝናናት እንዳይችል በልጅነቱ ከወላጆቹና
ከዘመዶቹ ካደገበት ቀዬ ነጥቀው በጭንቀት በሃዘን… እያለቀሰ!
ማንነታቸውን የማያውቃቸው ሰዎች እንደ
አውሬ ደስታውን
ገነጣጥለው በልተውበታል፡ ተስፋውን አምክነውበታል፧ ስሜቱን ጭምትርትር አድርገው አኮራምተውበታል፡፡ እድሜው እየጨመረ
በሄደ ቁጥር ከጠባሳው በታች ሊድን የማይችል የቁስሉ ጎሚ እየበረታበት መጣ። ራሱን ሊያክም ሞከረ ውስጡ ግን እያመረቀዘ በሰራ አካላቱ የስቃይ መርዙ ተሰራጨ፡
“አኜስ! ለምን ስቃዬን አትረጅልኝም ሁሌ ለሞን አሸናፊነት ትመርጫለሽ!"
“ሎካዬ! ተው እንዲህ ምርር አትበል ልለይህ አለመፈለጌ
ላንተ ካለማሰብ የመጣ ነው ብለህ ታስባለህ? እንደዚያማ ላለማሰብ
ሞክር" ብላ አንገቷን ሰበር ስታደርግ ሎካዬ ጠጋ ብሎ ፀጉሯን ደባበሰና፡-
“ይቅር በይኝ እሽ አብረን እንሄዳለን" ሲል ቀና ብላ
አይታው እንባዋ ከአይኖችዋ ረገፉ:: ሎካዬ ግን እንባዋን ማየቱ
ከብዶት ፀጉሯን ስሞ ወጣ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በተለያየ ቀለማት ያሸበረቁ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሜዳውን ሞልተው እክሮባት ሲያሳዩ እንደቆዩ እውቁ ጣሊያናዊ አቀንቃኝ
ከሙዚቃው ጋር አጣጥሞ ድምፁ ሲያስረቀርቀው በስቴዲየሙ ውስጥ
ያለው ህዝብ አድናቆቱን በጭብጨባ በፉጨት በጩኸት በጥሩንባ በከበሮ
ሲገልፅ ድምፃዊው አሳ እንደሚውጥ ትልቅ አሳ ፉን
ከፍቶ ሲዘፍን በስታዲየሙ ዙሪያ የተደገኑት ማጉያዎች ድምፁን አስተጋቡት:: አሁንም ጭብጨባ ጩኸት ደስታ ሁካታ ሆነ፤
ጭፈራው ቀለጠ፡ ርችት ተለኮሰ፡፡
ከዚያ ከያገሩ የመጡት ሯጮች ወደ መወዳደሪያው ቦታ ሲወጡ ተመልካቹ
ቆሞ በጭብጨባ
ተቀበላቸው፡፡ ከያገሩ
ስለተወከሉት ተወዳዳሪዎች ማንነት ጋዜጠኞች በየቋንቋው መዘርዘር
ቀጠሉ፡
አኜስ ሎካዬ ከሪናና የአኜስ ወንድም ከሴት ጓደኛው ጋር
ሮም ስታዲዬም ናቸው: ከሎካዬ በስተቀር ሁሉም ያጨበጭባሉ ብድግ ቁጭ ይላሉ ይለፈልፋሉ… ሎካዬ ግን በብዙ ሺ ህዝብ መሀል ሆኖ ያልማል የልጅነቱን ህይወት የወላጆቹን ቀዬ...
ተወዳዳሪዎች ተደረደሩ፤ ችቦው ተለኮሰ፤ ማራቶን የሮማ ማራቶን ተጀመረ፡
ከዚያ በስቴዲየሙ ውስጥ የጥቂት አትሌቶች ገድልና
በዛኔው ውድድርም ያሸንፉ ይሆናል የሚለው ግምት ተለፈፈ፡፡አውሮፓውያን አሜሪካውያን ሩቀ ምስራቆች የአሰለፏቸው
አትሌቶች መጠን በ ውድድር አፍሪካውያን ተወዳዳሪዎችም በተወሰኑ አትሌቶች መወከላቸው ተነገረ፡፡
ከክርስቶስ ልደት በፊት በአራት መቶ ዘጠና በፔርሽያና አቴና በተፈጠረው ድንገተኛ የጦር ወረራ ትንኮሳ የተደናገጡት
አቴናውያን ፊዲፒደስ የተባለውን ጀግና ስፖርት ላኩት: ፊዲፒደስም
ለሃምሳ ሰዓታት ካለ ምግብና መጠጥ ሩጦ መልዕክቱን አድርሶ
በመመለሱ ውጊያው ተጀመረ፡፡
የአምባገነኑ የፔርሺያ ኃይል
ግን የማታ ማታ ሟሾ የውጊያው ድል ፎክሮ ጦር አውድማ ከሄደው ከፔርሽያው መሪ
ከዳሪዮስ እጅ ወጥቶ አቴናውያን እጅ ገባ፡፡
የአቴና ፍቅር ያማለለው ጀግናው ሯጭና ተዋጊ
ፌዲፒደስም ያንን ያገሩን ታላቅ ድል ሲያይ ደስታ
ፈንቅሎት አቅጠበጠው ስለዚህ ያንን ታላቅ ድል ለወገኑ ለማብሰር ቂጤማ
የያዘች እርግቡን ህሊናው ቆጥ ላይ አስፍሮ ሀያ ሁለት ማይልስ ካለ እረፍት የተነሳውን ክቡር ቃል ሊያደርስ ሮጠ፡፡
ፊዲፒደስ ከተማ
ሲደርስ አካሉ ደክሞ ! ሕይወቱ የተንጠለጠለችው ጠንካራ ሞራሉ ላይ ነበርና ወገን ሊያገኝ ያን
እንደ አልማዝ የሚያንፀባርቅ ቃል እያከለከለከ “ቪክትሪ" ብሉ ቃሏን ብቻ አሰምቶ ህዝቡ ሲደሰት እሱ ግን ሕይወቱን ለአገሩ ድል ሰዋ እየሳቀ አንቀላፋ!
መልካም ሥራና እውነት
ግን ውሎ አድሮ ከትቢያ
መነሳታቸው የክብር ሥፍራቸውን መያዛቸው አይቀርምና በአስራ
ስምንት መቶ ዘጠና ስድስት ግሪኮች የፊዲፒደስን ውለታ ለመክፈልተ ተስማሙ፡፡ መልካሙ ስሙን ከመቃብር ውጭ ሊያውለበልቡት
አቀዱ! ስለዚህ ባምላካቸው መሪ በዜውስ ስም ሰይመው የኦለምፒክ
ማራቶን ጀመሩ… ያ የመልካም ስራ ሽቶ መዓዛም አለማችንን
አወዳት፡፡ ከዚያ የማራቶን ሩጫ ውድድር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንና በምዕራባውያን አገሮች በተለይ ሩጫን ዘመናዊ
ለማድረግ ሳይንሳዊ አሰለጣጠን ዘዴዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን አትሌቶች ከህፃንነታቸው ጀምሮ እየተመለመሉ ድንቅ
ተወዳዳሪዎችን ማፍራት መቻሉም ተናገረ፡፡
ሚዲያዎች ተወዳዳሪዎች የደረሱበትን ማን እየመራ
እንደሆነ ገለፁ፡፡የሚመራው አፍሪካዊ' ነው ሲባል ስለ ዘመናዊ የሩጫ አሰለጣጠን ዘዴ የሰማው ተመልካች ግራ የገባው መሰለ፡፡ብዙዎች ግን በማራቶን እሩጫ ትልቁ ዘዴ ትንፋሽን መጠበቅና ሃይልን እየቆጠቡ ቆይቶ የተወስነ ርቀት ሲቀር አፈትልኮ እንደ
ቀስት መወርወር ነው፡፡ ሲጀመር አካባቢ የቀደመ በስተመጨረሻ አትሌቶችን እየተሰናበተ ውራ ይወጣል' እየተባባሉ ተሳለቁ፡፡
ህዝቡን ከሚያዝናና ዝግጅቶች ጣልቃ ላይ የማራቶን ተወዳዳሪዎች ደረጃ እንደገና ተጠቀሰ:: አሁንም “አፍሪካዊው
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እንደተለመደው እቤቴ አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተዘርሬ በመተኛት ጣፋጮና ተወዳጇ ልጄ በቴሌግራም የላከችልኝን የእናቷን ዲያሪ በከፍተኛ ተመስጦና ውስጥን በሚሸረካክት የልብ ድማት ያለፈ ታሪኬን እያነበብኩ ነው፡፡
////
ማትሪክ በተቀበልን በአንድ ወር ውስጥ ለሰርግ ሽር ጉድ ተጀመረ..፡፡ለሠርጉ 15 ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ..፡፡በረሽ ጥፊ ጥፊ..ወይም እራስሽን አጥፊ የሚል ስሜት ይተናነቀኝ ጀመር...፡፡እስቲ በፈረሰኛው በግድ ካላገባሽ እቆራርጥሻለሁ ብሎ ያስፈራራኝ ሰው የለ... ሁሉንም ያደረኩት በራሴ ፍቃድና ምርጫ ነው። እንደውም ቤተሠቦቼ በዚህ ሀሳብ እንዲስማሙ ለማሳመን ብዙ ነገር ቀባጥሬ ነበር...እና ታዲያ ?የቁርጡ ቀን ሲመጣ ምነውሳ...?ዋናው ጉዳይ ከእዬቤ እንዴት አድርጌ የምር እለያለሁ ?የሚለው ሀሳብ ነው እረፍት የነሳኝ....፡፡ እርግጥ አውቃለሁ ወደ ጋብቻው የገባሁበት ዋና አላማ ከእዬብ ለመራቅ ከአምላክ የተላከ ልዩና ረቂቅ ዘዴ አድርጌ በደፈናው ተቀብዬው ነበር እንጂ ዝርዝር ጉዳዬች ላይ በደንብ ያሰብኩባቸው አልነበረም። ይታያችሁ ባል ካገባው እኮ አብሮ ማደር ከዛም ያለፈ ነገር ማድረግ የግድ ነው ፡፡ በህልሜም ሆነ በእውኔ ከእዬብ ገላ ውጭ የወንድ ገላ ታስቦኝ በፍፁም አያውቅም።የሚገርመው እናትና አባቴን ጨምሮ የቤቱ ሰው ሁሉ በደስታ ሰክሮ ለድግሱ መሳካት ጠብ እርግፍ ሲል እዬቤ ግን ልክ እንደእኔ በተመሳሳይ ሁኔታ ድባቴ ውስጥ ገብቶ ነበር።አሳዘነኝ።እሱም እንደ እኔ ያፈቅረኝ ይሆን እንዴ?ለመጀመሪያ ጊዜ በአእምሮዬ የተሠነቀረ አስደሳች ጥርጣሬ ነበር ፡፡
ለማንኛውም የሰርጉ ቀን ደረሰ በተክሊል ስለምንጋባ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ለሊት ስምንት ሰዓት ነው ቤተክርስቲያን የሄድነው። ግን በተክሊል እንዴት ልንጋባ ወሰንን? እርግጥ ሀሳብን ቀድሞ ያቀረበው መስፋን ነው።ግን እኔም ያለምንም ማቅማማት ነበር እሺ ያልኩት ፡፡ለዚህም ምክንያቴ በዋናነት ሁለት ነው። አንደኛው በተክሊል መጋባት ጋብቻውን ጥብቅ ስለሚያደርገው ወለም ዘለም የሚለውን ልቤን ያቃናልኛል ወይም መስመር ያስገባልኛል ብዬ ስላመንኩ ነው።ሁለተኛው ብዙ የሠንበት ት/ቤት ጓደኞቼ በተክሊል ሲያገቡ ሚዜም ሆነ አጃቢ ሆኚ አይቼ ስለነበረ እኔም አንድ ቀን እንደዚህ አገባ ይሆን የሚል የተደበቀ ምኞት በውስጤ ስለነበረ ያንን ምኞቴን ለማሳካት ያገኘሁትን እድል ለመጠቀም ነበር።
ስርዓቱም ከቅዳሴው ጥዋት ሶስት ሰዓት ተጠናቀቀ።በሰንበት ት/ቤት መዘምራን የሠርግ መዝሙር በመታጀብ ወደ የቤታችን ሄድን።እንግዲህ ምሳ ሰዓት ላይ ሙሽራው ከሚዜዎቹና አጃቢዎቹ ጋር መጥተው እስኪወስድን የተወሰነ ለማረፍና ለመዘገጃጀት የሚሆን ጊዜ ይኖረናል ብዬ ነው።እቤት ከገባን በኃላ ትንሽ ለማረፍ ሞከርኩ እንቅልፍ ሊወስደኝ ግን አልቻለም፡፡ ተነሳሁና እየተኳኳሉና እየተቆነጃጅ ካሉት ሚዜዎቼ ጋር ተቀላቀልኩ።እኔም መዘገጃጀት ስላለብኝ ያሳምሩኝ ጀመር...፡፡ሁሉም ደስተኛ ይመስላል... የተከፈተ ጥርስ..የፈገገ ፊት...በማይክራፎን የተለቀቀ መዝሙር እኔ ግን ቅር እንዳለኝ ነው ።ከቤተ ክርስቲያን መልስ ጀምሮ እዬቤን አላየሁትም።የት ገባ?ከአሁኑ በጣም ነው የናፈቀኝ።እህቴን ጠራኋትና ጠየቅኳት..እንዳላየችው ነገረችኝ።ሌላ የምትሰራውን ስራ ሁሉ ትታ እሱን ፈልጋ እንድትጠራልኝ ጠየቅኳት...ሌላ ቀን ቢሆን የራስሽ ጉዳይ ነበር የምትለኝ።በእለቱ ግን ያው የቤቱ ንግስት ነኝና ጥያቄዬን በእሺታ ተቀብላ ልትፈልገው ወጣች።
15 ከሚሆኑ ደቂቃዎች በኃላ ይመስለኛል እየተጎተተ በግድ የፈገገ ግን ደግሞ የዳመነ ፊቱን ይዞ መጣ..ሴቶች የሞሉበትን ክፍል በራፍ ላይ ቆሞ አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ‹‹ሪች ፈለግሺኝ" ሲል ጠየቀ….ገና ድምፁ ጆሮዬ ከመድረሱ ሰውነቴ በጠቅላላ ነዘረኝ፡፡
‹‹አዎ ግባ››
‹‹ወዴት ልግባ..?››
‹‹ጥፋሬን ቀለም እየተቀባሁ ስለሆነ እኮ ነው..ግባ የማታውቀው ሰው የለም "ብዬ አደፋፈርኩት፡፡ገባና ወደእኔ ቀረበ..እንዲቀመጥ ኩርሲ ከጎኔ አስቀመጥኩለት እያቅማማ ተቀመጠ።እዛች ክፍል ውስጥ የተጠቀጠቁት ሴቶች ጆሮና አይን በጠቅላላ እኛ ላይ እንደሰፈረ አውቃለሁ። ቢሆንም ምርጫ የለኝም።ድምፄን ቀነስ አድርጌ በሹክሹክታ መጠን
"የት ጠፍተህ ነው? ናፈቅከኝ እኮ"አልኩት
"ደክሞኝ ተኝቼ ነበር"
"የት?"ይህንን ጥያቄ የጠየቅኩት የእኔና የእሱን የጋራ ክፍል አሁን እያተረማመሰነው ስለሆነ ብዬ ነው፡፡
"እቴቴ ክፍል"
"አይንህ ግን ምንም የተኛ ሰው አይን አይመስልም"
እንደዛ ያልኩት አይኑ በርበሬ ይመስላል እንደሚባለው ቀይ ሆኖ ስለደፈራረሰ ነው።
"ተኝቼ ነበር እኮ አልኩሽ...አሁን ለምን ፈለግሺኝ?"ቆጣ አለ፡፡
"አትቆጣኛ"
"አልተቆጣሁሽም"
"አብረኸን ትሄዳለህ አይደል?"
ደንግጦ"የት?"
ለእሱ መልስ ከመመለሴ በፊት ‹‹ተነሡ ተነሱ ሰርገኛው ደረሰ ተዘጋጅ ..››የሚል የማንቂያ ድምፅ ከውጭ ተሰማ…ትርምስምስ ተፈጠረ... የእሱን አደነጋገጥ እስከዛሬም በፊቴ ላይ አለ።በርግጎ ተነስቶ ፊቴ ተገተረ...እኔም ተነስቼ ቆምኩ።ተጠመጠምኩበት..ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ።እንባዬን ዘረገፍኩት እሱም ተንሰቅስቆ ማልቀስ ጀመረ።ሊያላቅቁን መሀላችን ገቡ።
‹‹አረ ቆርበሽ እንዴት ታለቅሺያለሽ?››
"አገባች እንጂ አልሞተች… የምን ሟርት ነው?።››
"አረ ተው ነውር ነው።››
ሁሉም የመሰለውን ተንጣጣ...አላቀቁን ።እዬቤ ተስፈንጥሮ ክፍሉን ለቆ ተፈተለከ።ከፋኝ ።በጣም ከፋኝ።ፈፅሞ ጥሎኝ እንዲሄድ አልፈለኩም ነበር።እጥፍጥፍ አድርጌ ጡቶቼ መሀከል ከትቼ በየሄድኩበት ይዤው ብሄድ ደስተኛ ነበርኩ።..የምሳ ፕሮግራሙ ሲካሄድም ሆነ እኛ ቤት የነበረው ዝግጅት ተጠናቆ ከእኛ ቤት ወጥተን ስንሄድ አይኔ ቢንከራተትም እዬቤን ዳግመኛ ሳላየው ነበር የእናትና አባቴን ቤት ለዘላለም በሚመስል መንገድ ለቅቄ በቅርብ ከተዋወቅኩት እና በቅጡ እንኳን ያለመድኩትን ሰው ተከትዬ የሄድኩት።
ሙሽራው ሙሽሪት..እንኳን ደስ ያላችሁ
የአብርሀም የሳራ-ይሁን ጋብቻችሁ።
እንደዛ እንደዛ እያለ ሰርጉ ተጠናቀቀ ..መሸ ጫጉላ ቤት ገባን ..እግዚያብሄር ይመስገን ፡፡ በተክሊል ስለተጋባንና በእለቱም ስለቆረብኩ ግንኙነት ማድረግ አይፈቀድም ነበርና አንድ አልጋ ላይ ብንተኛም ሰውነታችንን እንኳን ሳናነካካ ተራርቀን ተኛን ፡፡የሁለት ቀን የተጠራቀመ እንቅልፍ ስለነበረብኝ የት እንዳደርኩ አላውቅም ነበረ ።የሚገርመው ጥዋት እንደነቃሁ በእጆቼ የሞጨሞጩ አይኖቼን እያሻሸው"እዬብ ነጋ እንዴ?"ብዬ ነበር ጠየቅኩት ።ደግነቱ ክፍል ውስጥ ማንም ስላልነበረ የሰማኝ ሰው አልነበረም። እንደምንም አልጋዬን ለቅቄ በመውረድ ልብሴን እየለበሰኩ ሳለ በሩ ተከፈተና መስፍኔ ገባ፡
"እንዴ ተነሳሽ እንዴ?"ዝም አልኩት።
"ምነው አመመሽ እንዴ?"አለኝ ወደእኔ እየተጠጋ።
ጭራሽ እየታገልኩት የነበረውን ስሜቴን ነቅንቆ አደፈራረሠው...እንባዬን ዘረገፍኩት።
"እንዴ ምነው?ምን ተፈጠረ?"
"እዬቤ"
"እዬቤ ምን ሆነ?››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
እንደተለመደው እቤቴ አልጋዬ ላይ በጀርባዬ ተዘርሬ በመተኛት ጣፋጮና ተወዳጇ ልጄ በቴሌግራም የላከችልኝን የእናቷን ዲያሪ በከፍተኛ ተመስጦና ውስጥን በሚሸረካክት የልብ ድማት ያለፈ ታሪኬን እያነበብኩ ነው፡፡
////
ማትሪክ በተቀበልን በአንድ ወር ውስጥ ለሰርግ ሽር ጉድ ተጀመረ..፡፡ለሠርጉ 15 ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ..፡፡በረሽ ጥፊ ጥፊ..ወይም እራስሽን አጥፊ የሚል ስሜት ይተናነቀኝ ጀመር...፡፡እስቲ በፈረሰኛው በግድ ካላገባሽ እቆራርጥሻለሁ ብሎ ያስፈራራኝ ሰው የለ... ሁሉንም ያደረኩት በራሴ ፍቃድና ምርጫ ነው። እንደውም ቤተሠቦቼ በዚህ ሀሳብ እንዲስማሙ ለማሳመን ብዙ ነገር ቀባጥሬ ነበር...እና ታዲያ ?የቁርጡ ቀን ሲመጣ ምነውሳ...?ዋናው ጉዳይ ከእዬቤ እንዴት አድርጌ የምር እለያለሁ ?የሚለው ሀሳብ ነው እረፍት የነሳኝ....፡፡ እርግጥ አውቃለሁ ወደ ጋብቻው የገባሁበት ዋና አላማ ከእዬብ ለመራቅ ከአምላክ የተላከ ልዩና ረቂቅ ዘዴ አድርጌ በደፈናው ተቀብዬው ነበር እንጂ ዝርዝር ጉዳዬች ላይ በደንብ ያሰብኩባቸው አልነበረም። ይታያችሁ ባል ካገባው እኮ አብሮ ማደር ከዛም ያለፈ ነገር ማድረግ የግድ ነው ፡፡ በህልሜም ሆነ በእውኔ ከእዬብ ገላ ውጭ የወንድ ገላ ታስቦኝ በፍፁም አያውቅም።የሚገርመው እናትና አባቴን ጨምሮ የቤቱ ሰው ሁሉ በደስታ ሰክሮ ለድግሱ መሳካት ጠብ እርግፍ ሲል እዬቤ ግን ልክ እንደእኔ በተመሳሳይ ሁኔታ ድባቴ ውስጥ ገብቶ ነበር።አሳዘነኝ።እሱም እንደ እኔ ያፈቅረኝ ይሆን እንዴ?ለመጀመሪያ ጊዜ በአእምሮዬ የተሠነቀረ አስደሳች ጥርጣሬ ነበር ፡፡
ለማንኛውም የሰርጉ ቀን ደረሰ በተክሊል ስለምንጋባ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ለሊት ስምንት ሰዓት ነው ቤተክርስቲያን የሄድነው። ግን በተክሊል እንዴት ልንጋባ ወሰንን? እርግጥ ሀሳብን ቀድሞ ያቀረበው መስፋን ነው።ግን እኔም ያለምንም ማቅማማት ነበር እሺ ያልኩት ፡፡ለዚህም ምክንያቴ በዋናነት ሁለት ነው። አንደኛው በተክሊል መጋባት ጋብቻውን ጥብቅ ስለሚያደርገው ወለም ዘለም የሚለውን ልቤን ያቃናልኛል ወይም መስመር ያስገባልኛል ብዬ ስላመንኩ ነው።ሁለተኛው ብዙ የሠንበት ት/ቤት ጓደኞቼ በተክሊል ሲያገቡ ሚዜም ሆነ አጃቢ ሆኚ አይቼ ስለነበረ እኔም አንድ ቀን እንደዚህ አገባ ይሆን የሚል የተደበቀ ምኞት በውስጤ ስለነበረ ያንን ምኞቴን ለማሳካት ያገኘሁትን እድል ለመጠቀም ነበር።
ስርዓቱም ከቅዳሴው ጥዋት ሶስት ሰዓት ተጠናቀቀ።በሰንበት ት/ቤት መዘምራን የሠርግ መዝሙር በመታጀብ ወደ የቤታችን ሄድን።እንግዲህ ምሳ ሰዓት ላይ ሙሽራው ከሚዜዎቹና አጃቢዎቹ ጋር መጥተው እስኪወስድን የተወሰነ ለማረፍና ለመዘገጃጀት የሚሆን ጊዜ ይኖረናል ብዬ ነው።እቤት ከገባን በኃላ ትንሽ ለማረፍ ሞከርኩ እንቅልፍ ሊወስደኝ ግን አልቻለም፡፡ ተነሳሁና እየተኳኳሉና እየተቆነጃጅ ካሉት ሚዜዎቼ ጋር ተቀላቀልኩ።እኔም መዘገጃጀት ስላለብኝ ያሳምሩኝ ጀመር...፡፡ሁሉም ደስተኛ ይመስላል... የተከፈተ ጥርስ..የፈገገ ፊት...በማይክራፎን የተለቀቀ መዝሙር እኔ ግን ቅር እንዳለኝ ነው ።ከቤተ ክርስቲያን መልስ ጀምሮ እዬቤን አላየሁትም።የት ገባ?ከአሁኑ በጣም ነው የናፈቀኝ።እህቴን ጠራኋትና ጠየቅኳት..እንዳላየችው ነገረችኝ።ሌላ የምትሰራውን ስራ ሁሉ ትታ እሱን ፈልጋ እንድትጠራልኝ ጠየቅኳት...ሌላ ቀን ቢሆን የራስሽ ጉዳይ ነበር የምትለኝ።በእለቱ ግን ያው የቤቱ ንግስት ነኝና ጥያቄዬን በእሺታ ተቀብላ ልትፈልገው ወጣች።
15 ከሚሆኑ ደቂቃዎች በኃላ ይመስለኛል እየተጎተተ በግድ የፈገገ ግን ደግሞ የዳመነ ፊቱን ይዞ መጣ..ሴቶች የሞሉበትን ክፍል በራፍ ላይ ቆሞ አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ‹‹ሪች ፈለግሺኝ" ሲል ጠየቀ….ገና ድምፁ ጆሮዬ ከመድረሱ ሰውነቴ በጠቅላላ ነዘረኝ፡፡
‹‹አዎ ግባ››
‹‹ወዴት ልግባ..?››
‹‹ጥፋሬን ቀለም እየተቀባሁ ስለሆነ እኮ ነው..ግባ የማታውቀው ሰው የለም "ብዬ አደፋፈርኩት፡፡ገባና ወደእኔ ቀረበ..እንዲቀመጥ ኩርሲ ከጎኔ አስቀመጥኩለት እያቅማማ ተቀመጠ።እዛች ክፍል ውስጥ የተጠቀጠቁት ሴቶች ጆሮና አይን በጠቅላላ እኛ ላይ እንደሰፈረ አውቃለሁ። ቢሆንም ምርጫ የለኝም።ድምፄን ቀነስ አድርጌ በሹክሹክታ መጠን
"የት ጠፍተህ ነው? ናፈቅከኝ እኮ"አልኩት
"ደክሞኝ ተኝቼ ነበር"
"የት?"ይህንን ጥያቄ የጠየቅኩት የእኔና የእሱን የጋራ ክፍል አሁን እያተረማመሰነው ስለሆነ ብዬ ነው፡፡
"እቴቴ ክፍል"
"አይንህ ግን ምንም የተኛ ሰው አይን አይመስልም"
እንደዛ ያልኩት አይኑ በርበሬ ይመስላል እንደሚባለው ቀይ ሆኖ ስለደፈራረሰ ነው።
"ተኝቼ ነበር እኮ አልኩሽ...አሁን ለምን ፈለግሺኝ?"ቆጣ አለ፡፡
"አትቆጣኛ"
"አልተቆጣሁሽም"
"አብረኸን ትሄዳለህ አይደል?"
ደንግጦ"የት?"
ለእሱ መልስ ከመመለሴ በፊት ‹‹ተነሡ ተነሱ ሰርገኛው ደረሰ ተዘጋጅ ..››የሚል የማንቂያ ድምፅ ከውጭ ተሰማ…ትርምስምስ ተፈጠረ... የእሱን አደነጋገጥ እስከዛሬም በፊቴ ላይ አለ።በርግጎ ተነስቶ ፊቴ ተገተረ...እኔም ተነስቼ ቆምኩ።ተጠመጠምኩበት..ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ።እንባዬን ዘረገፍኩት እሱም ተንሰቅስቆ ማልቀስ ጀመረ።ሊያላቅቁን መሀላችን ገቡ።
‹‹አረ ቆርበሽ እንዴት ታለቅሺያለሽ?››
"አገባች እንጂ አልሞተች… የምን ሟርት ነው?።››
"አረ ተው ነውር ነው።››
ሁሉም የመሰለውን ተንጣጣ...አላቀቁን ።እዬቤ ተስፈንጥሮ ክፍሉን ለቆ ተፈተለከ።ከፋኝ ።በጣም ከፋኝ።ፈፅሞ ጥሎኝ እንዲሄድ አልፈለኩም ነበር።እጥፍጥፍ አድርጌ ጡቶቼ መሀከል ከትቼ በየሄድኩበት ይዤው ብሄድ ደስተኛ ነበርኩ።..የምሳ ፕሮግራሙ ሲካሄድም ሆነ እኛ ቤት የነበረው ዝግጅት ተጠናቆ ከእኛ ቤት ወጥተን ስንሄድ አይኔ ቢንከራተትም እዬቤን ዳግመኛ ሳላየው ነበር የእናትና አባቴን ቤት ለዘላለም በሚመስል መንገድ ለቅቄ በቅርብ ከተዋወቅኩት እና በቅጡ እንኳን ያለመድኩትን ሰው ተከትዬ የሄድኩት።
ሙሽራው ሙሽሪት..እንኳን ደስ ያላችሁ
የአብርሀም የሳራ-ይሁን ጋብቻችሁ።
እንደዛ እንደዛ እያለ ሰርጉ ተጠናቀቀ ..መሸ ጫጉላ ቤት ገባን ..እግዚያብሄር ይመስገን ፡፡ በተክሊል ስለተጋባንና በእለቱም ስለቆረብኩ ግንኙነት ማድረግ አይፈቀድም ነበርና አንድ አልጋ ላይ ብንተኛም ሰውነታችንን እንኳን ሳናነካካ ተራርቀን ተኛን ፡፡የሁለት ቀን የተጠራቀመ እንቅልፍ ስለነበረብኝ የት እንዳደርኩ አላውቅም ነበረ ።የሚገርመው ጥዋት እንደነቃሁ በእጆቼ የሞጨሞጩ አይኖቼን እያሻሸው"እዬብ ነጋ እንዴ?"ብዬ ነበር ጠየቅኩት ።ደግነቱ ክፍል ውስጥ ማንም ስላልነበረ የሰማኝ ሰው አልነበረም። እንደምንም አልጋዬን ለቅቄ በመውረድ ልብሴን እየለበሰኩ ሳለ በሩ ተከፈተና መስፍኔ ገባ፡
"እንዴ ተነሳሽ እንዴ?"ዝም አልኩት።
"ምነው አመመሽ እንዴ?"አለኝ ወደእኔ እየተጠጋ።
ጭራሽ እየታገልኩት የነበረውን ስሜቴን ነቅንቆ አደፈራረሠው...እንባዬን ዘረገፍኩት።
"እንዴ ምነው?ምን ተፈጠረ?"
"እዬቤ"
"እዬቤ ምን ሆነ?››
#ባል_አስይዞ_ቁማር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ልዩ ቃል ቤት ነው ያለችው….እየሳቁና እየተጫወቱ ሳለ ድንገት በራፍ ተንኳኳ
"ቆይ አንዴ..›› አለና ሄዶ ከፈተ::
"እንዴ ጊፍቲ ከየት ተገኘሽ?"ጎትቶ አስገባትና እቅፉ ውስጥ ሸጎጦ አወዛወዛት፡፡
በተቀመጠችበት ወንበር ወደ ውስጥ እየሠመጠባት ያለ መስሎ ተሠማት.. ‹‹ፍቅረኛው ይህቺ ነች ማለት ነው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡ከአመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንጀቷ ፀለየች.. "እባክህ አምላኬ..ምን አለ እጮኛው ከምትሆን እህቱ ሆና በሆነ..››ደግሞ በምናቧ ከሳለቻት በላይ ቆንጆ ሆና ታየቻት…‹‹ ከእሱ ጋር አንድ ላይ ሲታዩ መንታ እህቱ ነው የምትመስለው"አለች
ቃል ጊፍቲን አቅፎ ብቻ አልበቃውም ጉንጯን እያገላበጠ ሳመትና ወደእሷ ይዞት መጣ...
ከእሷ አንድ ሶስት አመት በለጥ ትላለች ..እንደእሱ ጥንቅቅ ያለች ነገር ነች።‹‹ልዩ ተዋወቂያት ..ጊፋቲ ማለት በጣሞ የምወዳት የልጅነት ጓደኛዬ ነች"..
ልዩ እጮኛዬ ነች ይላል ብላ ነበር የጠበቀችው… ጓደኛዬ ነች ስላላት ደስ አለት…ከተቀመጠችበት እንደመነሳት ብላ እጇን ለሠላምታ ዘረጋችላት፤እሷም በተመሳሳይ ድንግርግር ያለ ስሜት ላይ ያለች ይመስላል.. .የዘረጋችላትን እጇን በስሱ ጨበጠችና‹‹ ጊፍቲ እባላለሁ"አላቻት።
"ልዪ"
ሁለቱም ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀመጡ
ቃል "ሱቅ ደርሼ መጣሁ..ተጫወቱ›› ብሎቸው ወጥቶ ሄደ..ይሄንን ያደረገው ሆነ ብሎ ነው…
በራፉን አልፎ ከአይናቸው እስኪሰወር ሁለቱም አይናቸው እየተንከራተተ ነበር።ለሆኑ ደቂቃዎች በዝምታ ከተገማገምን በኃላ ጊፍቲ ቅድሚያውን ወስደ ‹‹"ከቃልዬ ጋር እንዴት ተዋወቃችሁ...?የመስሪያ ቤት ጓደኛው ነሽ?"ስትል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡
"ቃልዬ" ብላ ስትጠራው ቃሉ አፎ ውስጥ ሚቀልጥ ነው የሚመስለው
ልዩም ‹‹…አይ የስራ ባለደረባው አይደለሁም ...ጓደኛው ነኝ"አለቻት ኮስተር ብላ.. ነገር አጨመላልቃለሁ ብላ ነው እንጂ ‹‹ፍቅረኛው ነኝ›› ልትላት ሁሉ ቃጥቷት ነበር፡፡
ጊፍቲ "ጓደኛው..."አለች በማሽሞጠጥ ቃና፡፡
"እ ምነው ...?ችግር አለው?"
"አረ በፍፅም የእኔ ቆንጆ...ብቻ የቃልዬ ነገር ይገርመኛል… ከልጅነታችን ጀምሮ በየጊዜው አዳዲስ ጓደኞች በማፍራት እንዳስገረመኝ ነው...ይሄው ለስራ ጉዳይ ለአንድ ወር ከስሩ ዞር ስል አንቺን የመሰለች አዲስ ጓደኛ አፍርቶ ጠበቀኝ።"
ልዩ ይህቺን ሴት ጠላቻት ‹‹..አሮጊት ነገር ነች .. እዩት በአንድ አረፍተነገር መናገር የፈለገችውን ሁሉ ስትናገር...ከልጅነት ጀምሮ እንደሚተዋወቁ...የእኔ እና የእሱ ትውውቅ ደግሞ ከአንድ ወር በላይ ዕድሜ እንደሌለው እርግጠኛ እንደሆነች አሳወቀቺኝ።›› ስትል በውስጧ ስለጊፍቲ ንግግር የተሰማትን አብሰለሰለች፡፡
የመቆየት አፕታይቷ ተዘጋ...ቦርሳዋን ያዝችና ከመቀመጫዋ ተነሳች...፡፡
"እንዴ ምነው..?ቃልዬ ሳይመጣ ልትሄጂ ነው…ብና ወይ ሻይ ላፈላልሽ ነበር አኮ …?"አለቻት..ከፊቷ መፈገግ የሚናገረው ግን ተቃራኒውን ነው፡፡አዎ ጊፍቲ በልዩ መሄድ በጣም ደስተኛ እንደሆነች ነው፡፡
"በፊትም ልሄድ ስል ነው የመጣሺው...ቀጠሮ አለብኝ…ሻይ ደግሞ እደመጣሁ ነው ቃል አፍልቶ የጠጣነው"አለቻት…እንደዛ ስትል ቃል ቢሰማ ምን ሊያስብ እንደሚችል ታሰባትና ሽምቅቅ አለች...ምክንያቱም ከመጣች መምንም አይነት ሻይም ሆነ ቡና አልቀመሱም፡፡
"ካልሽ እሺ..አትጥፊ እዚህ ስትመጪ ታገኚኛለሽ"አለቻት…እሷስ መች የዋዛ…‹‹ለምን እዚህ ብቻ የቃል ጓደኛ ከሆንሽ የእኔም ጓደኛ ነሽ..ቁጥርሽን ስጪኝና እንደዋወል"
ቁጥሯን መስጠቷን እንዳልፈለገችው በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ "ይሻላል"አለቻት...
ልዩ ግግም አለችባት...በውስጧ‹‹እንደው ከእዚህ ወጥቼ ባልደውልላት እንኳን እንዳበሳጨቺኝ ላበሳጫት።››ብላ ነው፡፡
ጊፍቲም እንደማትለቃት ሲገባት ቶሎ እንድትወጣላት የፈለገች መሆኗን በሚያሳብቅ ፍጥነት ጥድፍ ጥድፍ ብላ ነገረቻት።
ጎንበስ ብላ ጉንጯን ሳመችትና ‹‹ቃልን እንዲህ ስመሽ ይቅርታ ጠይቂልኝ...ላንቺ ሰሞኑን ደውልልሻለሁ"
ጊፍቲ ምን እንደምትመልስልኝ በማሰላሠል ላይ እያለች ፈጠን ብላ እቤቱን ለቃ ወጣች።መኪናዋን ከጊቢ ውጭ ስላቆመች ቀጥታ ወደእዛ ሄዳ ለጠበቀላት ሊስትሮ ትንሽ ሳንቲም አስጨብጣ ቃል መንገድ ላይ አግኝቶ በጥያቄ እ ንዳያጣድፋት ስለፈለገች ፈጠን ብላ ሰፈሩን ለቃ ወጣች፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ልዩ ቃል ቤት ነው ያለችው….እየሳቁና እየተጫወቱ ሳለ ድንገት በራፍ ተንኳኳ
"ቆይ አንዴ..›› አለና ሄዶ ከፈተ::
"እንዴ ጊፍቲ ከየት ተገኘሽ?"ጎትቶ አስገባትና እቅፉ ውስጥ ሸጎጦ አወዛወዛት፡፡
በተቀመጠችበት ወንበር ወደ ውስጥ እየሠመጠባት ያለ መስሎ ተሠማት.. ‹‹ፍቅረኛው ይህቺ ነች ማለት ነው?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡ከአመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአንጀቷ ፀለየች.. "እባክህ አምላኬ..ምን አለ እጮኛው ከምትሆን እህቱ ሆና በሆነ..››ደግሞ በምናቧ ከሳለቻት በላይ ቆንጆ ሆና ታየቻት…‹‹ ከእሱ ጋር አንድ ላይ ሲታዩ መንታ እህቱ ነው የምትመስለው"አለች
ቃል ጊፍቲን አቅፎ ብቻ አልበቃውም ጉንጯን እያገላበጠ ሳመትና ወደእሷ ይዞት መጣ...
ከእሷ አንድ ሶስት አመት በለጥ ትላለች ..እንደእሱ ጥንቅቅ ያለች ነገር ነች።‹‹ልዩ ተዋወቂያት ..ጊፋቲ ማለት በጣሞ የምወዳት የልጅነት ጓደኛዬ ነች"..
ልዩ እጮኛዬ ነች ይላል ብላ ነበር የጠበቀችው… ጓደኛዬ ነች ስላላት ደስ አለት…ከተቀመጠችበት እንደመነሳት ብላ እጇን ለሠላምታ ዘረጋችላት፤እሷም በተመሳሳይ ድንግርግር ያለ ስሜት ላይ ያለች ይመስላል.. .የዘረጋችላትን እጇን በስሱ ጨበጠችና‹‹ ጊፍቲ እባላለሁ"አላቻት።
"ልዪ"
ሁለቱም ፊት ለፊት ተፋጠው ተቀመጡ
ቃል "ሱቅ ደርሼ መጣሁ..ተጫወቱ›› ብሎቸው ወጥቶ ሄደ..ይሄንን ያደረገው ሆነ ብሎ ነው…
በራፉን አልፎ ከአይናቸው እስኪሰወር ሁለቱም አይናቸው እየተንከራተተ ነበር።ለሆኑ ደቂቃዎች በዝምታ ከተገማገምን በኃላ ጊፍቲ ቅድሚያውን ወስደ ‹‹"ከቃልዬ ጋር እንዴት ተዋወቃችሁ...?የመስሪያ ቤት ጓደኛው ነሽ?"ስትል ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡
"ቃልዬ" ብላ ስትጠራው ቃሉ አፎ ውስጥ ሚቀልጥ ነው የሚመስለው
ልዩም ‹‹…አይ የስራ ባለደረባው አይደለሁም ...ጓደኛው ነኝ"አለቻት ኮስተር ብላ.. ነገር አጨመላልቃለሁ ብላ ነው እንጂ ‹‹ፍቅረኛው ነኝ›› ልትላት ሁሉ ቃጥቷት ነበር፡፡
ጊፍቲ "ጓደኛው..."አለች በማሽሞጠጥ ቃና፡፡
"እ ምነው ...?ችግር አለው?"
"አረ በፍፅም የእኔ ቆንጆ...ብቻ የቃልዬ ነገር ይገርመኛል… ከልጅነታችን ጀምሮ በየጊዜው አዳዲስ ጓደኞች በማፍራት እንዳስገረመኝ ነው...ይሄው ለስራ ጉዳይ ለአንድ ወር ከስሩ ዞር ስል አንቺን የመሰለች አዲስ ጓደኛ አፍርቶ ጠበቀኝ።"
ልዩ ይህቺን ሴት ጠላቻት ‹‹..አሮጊት ነገር ነች .. እዩት በአንድ አረፍተነገር መናገር የፈለገችውን ሁሉ ስትናገር...ከልጅነት ጀምሮ እንደሚተዋወቁ...የእኔ እና የእሱ ትውውቅ ደግሞ ከአንድ ወር በላይ ዕድሜ እንደሌለው እርግጠኛ እንደሆነች አሳወቀቺኝ።›› ስትል በውስጧ ስለጊፍቲ ንግግር የተሰማትን አብሰለሰለች፡፡
የመቆየት አፕታይቷ ተዘጋ...ቦርሳዋን ያዝችና ከመቀመጫዋ ተነሳች...፡፡
"እንዴ ምነው..?ቃልዬ ሳይመጣ ልትሄጂ ነው…ብና ወይ ሻይ ላፈላልሽ ነበር አኮ …?"አለቻት..ከፊቷ መፈገግ የሚናገረው ግን ተቃራኒውን ነው፡፡አዎ ጊፍቲ በልዩ መሄድ በጣም ደስተኛ እንደሆነች ነው፡፡
"በፊትም ልሄድ ስል ነው የመጣሺው...ቀጠሮ አለብኝ…ሻይ ደግሞ እደመጣሁ ነው ቃል አፍልቶ የጠጣነው"አለቻት…እንደዛ ስትል ቃል ቢሰማ ምን ሊያስብ እንደሚችል ታሰባትና ሽምቅቅ አለች...ምክንያቱም ከመጣች መምንም አይነት ሻይም ሆነ ቡና አልቀመሱም፡፡
"ካልሽ እሺ..አትጥፊ እዚህ ስትመጪ ታገኚኛለሽ"አለቻት…እሷስ መች የዋዛ…‹‹ለምን እዚህ ብቻ የቃል ጓደኛ ከሆንሽ የእኔም ጓደኛ ነሽ..ቁጥርሽን ስጪኝና እንደዋወል"
ቁጥሯን መስጠቷን እንዳልፈለገችው በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ "ይሻላል"አለቻት...
ልዩ ግግም አለችባት...በውስጧ‹‹እንደው ከእዚህ ወጥቼ ባልደውልላት እንኳን እንዳበሳጨቺኝ ላበሳጫት።››ብላ ነው፡፡
ጊፍቲም እንደማትለቃት ሲገባት ቶሎ እንድትወጣላት የፈለገች መሆኗን በሚያሳብቅ ፍጥነት ጥድፍ ጥድፍ ብላ ነገረቻት።
ጎንበስ ብላ ጉንጯን ሳመችትና ‹‹ቃልን እንዲህ ስመሽ ይቅርታ ጠይቂልኝ...ላንቺ ሰሞኑን ደውልልሻለሁ"
ጊፍቲ ምን እንደምትመልስልኝ በማሰላሠል ላይ እያለች ፈጠን ብላ እቤቱን ለቃ ወጣች።መኪናዋን ከጊቢ ውጭ ስላቆመች ቀጥታ ወደእዛ ሄዳ ለጠበቀላት ሊስትሮ ትንሽ ሳንቲም አስጨብጣ ቃል መንገድ ላይ አግኝቶ በጥያቄ እ ንዳያጣድፋት ስለፈለገች ፈጠን ብላ ሰፈሩን ለቃ ወጣች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ተአምራተ_ኬድሮን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ኬድሮን ካደረገቻቸው ሀገር አቋረጭ ጉዞዋች ውስጥ በጣም ድንቁና በህይወቷ መቼም የማተረሳው ወደታንዛኒያ ያደረገችው ጉዞ ነው ፡፡15 ዓመት ስትደፍን ሙሉ ወጣት ሴት ሆነች..የሰውነቷ ግዝፈትና የቁመቷ መመዝ ብቻ ሳይሆን የውበቷም መድመቅና መጉላት በሰፈሯም ብቻ ሳይሆን በከተማዋም በቀላሉ ሚለይና ልክ እንደሰንደቅ ምልክት ሆና መታየት ጀመረች…ከንስሯ ጋር ያለት መናበብና ቁርኝት በቃላትም የሚገለፅ አይነት አይደለም፡፡በተለይ የፈለገችውን ቦታ ወስዶ ስለሚያዝናናትና ስለሚሳያት በጣም ደስተኛ ብቻ ሳይሆን ስለአለም ያላት ግንዛቤና ስለተፈጥሮ ያላት ዕውቀት በጣም ጥልቅና በመገረም የተሞላ ሆነ ፡፡በትምሀርቷም በቀላሉ በሳምንት ሶስትና አራት ቀን ብቻ ክፍል ገባታ እየተማረች በትምህርት ቤቱ ታሪክ ታይታ የማታውቅ ኳከብና ተወዳጅ ተማሪ ሆነች፡አንደኛ ሴሚስተር ፈተና እንደተፈተነችና ትምህርት ቤት ለሳምንት እንደተዘጋ ረዘም ያለ ጉዞ ልትሄድ አሰበች፡ብዙ ቦታ በእምሮዋ መጥተው ነበር፤መጨረሻ ግን የአፍሪካ ጣሪያ በመባል ሚታወቀው ኪሊማንጀሮ ተራራን ሄዳ ለማየት ወሰነች፡፡ለእናቷ ለሶስት ቀን እንደማትኖር ተናገረችና በአነስተኛ ሻንጣ አንድ ሁለት ቀሚስና ፎጣ ነገር ያዘች… ዝግጁ ሆና ተነሳች..እናትዬው ወ.ሮ በሬዱ በመካከለኛ መጠን ባለው አገልግል የተጠቀጠቀ ጩኮ አስያዘቻት፡፡
‹‹እማ አሁን እኔና ንስሬ የምንራብ ይመስልሻል?››
‹ገራ ኮ እንደማይርባችሁ አውቀለሁ… .ግን ደግሞ ከእሱ ጋር ስጋ እየተናጠቁ መመገብ ብቻ ጤነኛ አመጋገብ አይሆንልሽም..አንቺ የእኔ ልጅ ነሽ …ሰው ነሽ እና እህልም በመጠኑም ቢሆን ሰውነትሽ ማግኘት አለበት፡››
‹እሺ እማ..ብላ የእናቷን ጉንጭ ስማ ንሰሯን አቅፋ ሻንጣዋን በአንድ ትከሻዋ አገልግሏን ደግሞ በሌላዋ ትከሻዋ በማንጠልጠል ንስሯን ከደረቷ አስጠግታ በጡቶቾ መካከል ለጥፋ ከሰፈር ወጥታ ሄደች… የያዘችው አቅጣጫ ወደምትሄድበትን የሚያመራ አይደለም….ስለዛ የምትጨነቅበት ምንም ምክንያት የለም…እሷ ሰፈሯን ለቃ ጭር ወደ አለ ጫካ ስፍራ ለመድረስ ነው እቅዷ.. ከዛ ንስሯን በአየር ላይ ለቀቀችው …ተርገፍግፎ ወደ ላይ በረረና አየሩን እየሰነጠቀ የተወሰነ ርቀት እየተገለባበጠ ለህዝቡ ትሪኢት እንደሚያሳይ የአንድ ሀገር አየር ኃይል ጀቶች የመከረባት ትርኢት አሳየና ወደእሷ እየተምዘገዘገ መጣ‹‹…ሰውነትህን እያሞሞቅክ መሆኑ ነው ›ስትል ፈገግ አለች…እሷ ግን ለእሷ ፈገግታ ምላሽ ሳይሰጥ በተለመደው ሁኔታ ማጅራቷ አካባቢ የለበሰችውን ልብስ ያዘና ከተሸከመችው ሻንጣና አገልግል ጋር አንድ ላይ በአየር ላይ አንጠለጠላትና ሽምጥ ወደላይ ተመነጠቀ…ከዛ በተለመደው ዘዴ ወደ ላይ ወርውሮ እየተምዘገዘገች ወደታች ስትወርድ ከኃላዋ ዞረና ጀርባዋ ላይ ተጣበቀባት…ከዛ ክንፍ ሆናት ማለት ነው፡፡ ከዛ በኃላ አቅጣጫውን ወደ ደቡብ አስተካክላት እሷም በተዝናኖት መብረር ጀመረች ፤መዳወላቡን ፤ነጌሌ ቦረናን፤ ሞያሌን በሩቁና በጭልጭልታ እያየች የኢትየጵያን ድንበር አቆርጠው ኬንያ ገቡ..የተወሰነ እንደተጎዙ በጣም ቀልብ ሚስብ ቦታ እይታዋ ውስጥ ገባ፡፡
ጀግናዬ እዛ ቦታ አረፍ ብንል ምን ይመስልሀል? ስትለው ከፍታውን እየቀነሰ ወደጎን እየተጎዘ ሄደና 20 የሚሆኑ ዝሆኖች ጀርባ ላይ ቁጭ አደረጋት ከጀርባዋ ተገንጥሎ ተለየና በራሱ መብረር ጀመረ .ደነገጠች.እሱ ከጭንቅላቷ በላይ በአምስት ሜትር እርቀት እየዞራት ነው፡፡ዝሆኑ እላዩ ላይ ዝንብ ያረፈበትም ሳይመስል ተረጋግቶ ከመሰሎቹ ጋር ወደፊት ጎምለል ጎምለል እያለ ይጓዛል…እሷ መረጋጋት አልቻለችም.. ዘላ እንዳትወርድ ከግራም ሆነ ከቀኝ መአት ዝሆኖች ናቸው ያሉት መሬት አርፋ ተስተካክላ ከመቆሞ በፊት በግዙፈ እግሮቻቸው ሚጨፈልቋት መስሎ ተሰማት...እራሷን በጣም ግዙፍና የሰማይ ስባሪ አድርጋ ትቆጥር ነበር.አሁን ከከበቧት ዝሆኖች ጋር እራሷን ስታነፃፅር ግን በዳዴ ሚሄድ ህጸን ልጅ የሆነች መስሎ ተሰማት፡፡
‹‹ጀግናዬ ና አንሳኝ ብዬሀለው. ና››
ንሰሯ ላይ ጮኸችበት …እየተመዘገዘገ ወደእሷ መጠና ትከሻዋን በክንፎቹ ቸብ አድርጎት መልሶ ወደላይ ተነሳ
‹‹አንተ ጫወታ ነው እንዴ የያዝከው ?ስወድህ….?የእኔ ጀግና በእኔ ትጨክናለህ….አላሳዝንህም››ተለማመጠችው፡፡
መልሶ ተከርብቶ መጣና ማጅራቷን ይዞ ወደ ላይ ተነሳና ከዝሆኖቹ መንጋ 20 ሜትር ያህል ራቅ አድርጎ ለምለም ሳር መካከል ቁጭ አደረጋት፡፡ግራና ቀኝ ትከሻዋ ላይ ያለውን ሻንጣዋንና አገልግሏን ከላዮ ላይ አውልቃ ጥላ በጀርባዋ ተዘረረች…ወደ ውስጧና ወደውጭ ደጋግማ አየር እየሰባች ወደውጭ በመልቀቅ ውስጧ በንፅህ አየር ብቻ ሳይሆን መረጋጋትም እንዲነግስባት መሞከር ጀመረች…ንስሯ ከጎኗ መጥቶ ተረጋግጦ ተቀመጠ
ለመረገጋጋት 10 ደቂቃ ያህል ከወሰደች በኃላ
አሁን ያረፉት መርሳቤት ብሄራዊ ፓርክ ነው፡፡ፓርኩ ከናይሮቢ 540ሜትር በስተሰሜን አርቆ ሚገኝ አጠቃላይ ስፋቱ 600 ሜ.እስኬር ስፋት ያለው በመርሳቤት ተራራ ማሀከል አድርጎ በሰሜን ኬንያ የሚገኘው ድንቅ ቦታ ኬድሮንና ንስሯ ከዚህ በፊትም አዘውትረው የሚጎበኙት በጣም ተመራጭ ስፍራቸው ነበር.ይህ ከእኛው ሞያሌ በቅርብ እርቀት ላይ የሚገኘው ፓርክ በልዩ ተፈጥሮ የበለፀገ ስፍራ ነው፤፤ቦታው በጥቅጥቅ ደን የተሸፈነ፤ 3 ሀይቆች ያሉት በተለይ ወፎችን በተመለከተ መነኸሪያቸው ነው ማለት ይቻላል.. ብዛታቸው የማይቆጠር ቀለምና አይነታቸው አስደማሚ ብቻ ሳይሆን ልብንም ስልብ የሚያደርግ ነው፤ከወፎች ቀጥሎ ዝሆኖች በብዛትና በምቾት የሚንጎማለሉበት ስፍራ ነው፡:
ልክ ስምንት ሰዓት ሲሆን አካባቢውን ለቀው ወደ ደቡብ ኬንያ ጉዞቸውን ቀጠሉ…የሚገኙበት በሌላ ጎን በአፍሪካም ሆነ በሀገረ ታንዛኒያ ሁለተኛው ረጅሙ ተራራ ከባህር ጠል በላይ 4566 ኪ.ሜት የሚረዝመው ሜሩ ብለው ሚጠሩት ተራራ የሚገኝበት የሚንዠቀዠቁ ያዶትን እና ዋቤ ሸበሌን መሰል ወንዞች የሚገኙበት የተፈጥሮ ገፀበረከት ቢፌ የሆነ ቦታ ነው ግን በመጠን ብዙም ሰፊ ያለሆነ አርሻ የሚባል ብሄራዊ ፓርክ ነው ከዛ ድንገት ኪሊ ማጀሮ ተራራ ትዝ አላት
አካባቢውን እስኪበቃቸው ከጎበኙና በኃላ ንስሯ እስከፈለገው ጥግ ያለማቆርጥ የመጓዝ ችግር ባይኖርባትም እሷ ከድካሟ የተነሳ ሰውነቷ ስለዛለ ከዛ በላይ መጓዝ አልፈለግችም..በአካባቢው ቅርብ ወደአለ ከተማ ሔደው ማደር ቢችሉም ግን ደግሞ በተለየ ለንስሯ ደህንነት አሳሳቢ ከመሆኑም በተጨማሪ ለእሷ ለራሷም ወደሰው ሀገር ለመግባት የሚያስችል ምንም አይነት ቢዛም ሆነ ፍቃድ ስሌላት እንደዛ ማድረግ አልመረጠች፣
‹‹ጀግናዬ እዚሁ ነው የምናድረው… ዞር ዞር ብለህ እራትህ ፈልግና ና.. እኔ የእናቴን ጩኮ በዚህች ምንጭ ውሀ እያወራረድኩ እበላለሁ›› አለችው…ትዕዛዟን አክብሮ በረረ …እሷም በያዘችው ኮዳ እየተንኳለለ ከሚወርደው የምንጭ ውሀ ቀዳችና በአካባቢው ከሚገኝ ግዙፍ ዛፍ ስር ተጠግታ አረፍ በማለት አገልግሏን ከፈተች…ውስጡ በባለው ማንኪያ እየቆረሰች በቂቤ ተነክሮ የተሰረራውን የእናቷን ተወዳጅ ምግብ በደስታ እያጣጠመች በልታ..ሳትጨርስ ንስሯ የራሱን ግዳይ በመንቁሩ አንገቱን አንቆ ይዞ መጣና ሰሯ አረፈ …ከዛ መሞቱን ካረጋገጠ እየዘነጣጠለ እስፈሪ በሆነ መንገድ መብላት ጀመረ
‹‹አረ ቀስ በል…..የት ትሄዳለህ?››አለችው፡፡
✨ይቀጥላል✨
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
///
ኬድሮን ካደረገቻቸው ሀገር አቋረጭ ጉዞዋች ውስጥ በጣም ድንቁና በህይወቷ መቼም የማተረሳው ወደታንዛኒያ ያደረገችው ጉዞ ነው ፡፡15 ዓመት ስትደፍን ሙሉ ወጣት ሴት ሆነች..የሰውነቷ ግዝፈትና የቁመቷ መመዝ ብቻ ሳይሆን የውበቷም መድመቅና መጉላት በሰፈሯም ብቻ ሳይሆን በከተማዋም በቀላሉ ሚለይና ልክ እንደሰንደቅ ምልክት ሆና መታየት ጀመረች…ከንስሯ ጋር ያለት መናበብና ቁርኝት በቃላትም የሚገለፅ አይነት አይደለም፡፡በተለይ የፈለገችውን ቦታ ወስዶ ስለሚያዝናናትና ስለሚሳያት በጣም ደስተኛ ብቻ ሳይሆን ስለአለም ያላት ግንዛቤና ስለተፈጥሮ ያላት ዕውቀት በጣም ጥልቅና በመገረም የተሞላ ሆነ ፡፡በትምሀርቷም በቀላሉ በሳምንት ሶስትና አራት ቀን ብቻ ክፍል ገባታ እየተማረች በትምህርት ቤቱ ታሪክ ታይታ የማታውቅ ኳከብና ተወዳጅ ተማሪ ሆነች፡አንደኛ ሴሚስተር ፈተና እንደተፈተነችና ትምህርት ቤት ለሳምንት እንደተዘጋ ረዘም ያለ ጉዞ ልትሄድ አሰበች፡ብዙ ቦታ በእምሮዋ መጥተው ነበር፤መጨረሻ ግን የአፍሪካ ጣሪያ በመባል ሚታወቀው ኪሊማንጀሮ ተራራን ሄዳ ለማየት ወሰነች፡፡ለእናቷ ለሶስት ቀን እንደማትኖር ተናገረችና በአነስተኛ ሻንጣ አንድ ሁለት ቀሚስና ፎጣ ነገር ያዘች… ዝግጁ ሆና ተነሳች..እናትዬው ወ.ሮ በሬዱ በመካከለኛ መጠን ባለው አገልግል የተጠቀጠቀ ጩኮ አስያዘቻት፡፡
‹‹እማ አሁን እኔና ንስሬ የምንራብ ይመስልሻል?››
‹ገራ ኮ እንደማይርባችሁ አውቀለሁ… .ግን ደግሞ ከእሱ ጋር ስጋ እየተናጠቁ መመገብ ብቻ ጤነኛ አመጋገብ አይሆንልሽም..አንቺ የእኔ ልጅ ነሽ …ሰው ነሽ እና እህልም በመጠኑም ቢሆን ሰውነትሽ ማግኘት አለበት፡››
‹እሺ እማ..ብላ የእናቷን ጉንጭ ስማ ንሰሯን አቅፋ ሻንጣዋን በአንድ ትከሻዋ አገልግሏን ደግሞ በሌላዋ ትከሻዋ በማንጠልጠል ንስሯን ከደረቷ አስጠግታ በጡቶቾ መካከል ለጥፋ ከሰፈር ወጥታ ሄደች… የያዘችው አቅጣጫ ወደምትሄድበትን የሚያመራ አይደለም….ስለዛ የምትጨነቅበት ምንም ምክንያት የለም…እሷ ሰፈሯን ለቃ ጭር ወደ አለ ጫካ ስፍራ ለመድረስ ነው እቅዷ.. ከዛ ንስሯን በአየር ላይ ለቀቀችው …ተርገፍግፎ ወደ ላይ በረረና አየሩን እየሰነጠቀ የተወሰነ ርቀት እየተገለባበጠ ለህዝቡ ትሪኢት እንደሚያሳይ የአንድ ሀገር አየር ኃይል ጀቶች የመከረባት ትርኢት አሳየና ወደእሷ እየተምዘገዘገ መጣ‹‹…ሰውነትህን እያሞሞቅክ መሆኑ ነው ›ስትል ፈገግ አለች…እሷ ግን ለእሷ ፈገግታ ምላሽ ሳይሰጥ በተለመደው ሁኔታ ማጅራቷ አካባቢ የለበሰችውን ልብስ ያዘና ከተሸከመችው ሻንጣና አገልግል ጋር አንድ ላይ በአየር ላይ አንጠለጠላትና ሽምጥ ወደላይ ተመነጠቀ…ከዛ በተለመደው ዘዴ ወደ ላይ ወርውሮ እየተምዘገዘገች ወደታች ስትወርድ ከኃላዋ ዞረና ጀርባዋ ላይ ተጣበቀባት…ከዛ ክንፍ ሆናት ማለት ነው፡፡ ከዛ በኃላ አቅጣጫውን ወደ ደቡብ አስተካክላት እሷም በተዝናኖት መብረር ጀመረች ፤መዳወላቡን ፤ነጌሌ ቦረናን፤ ሞያሌን በሩቁና በጭልጭልታ እያየች የኢትየጵያን ድንበር አቆርጠው ኬንያ ገቡ..የተወሰነ እንደተጎዙ በጣም ቀልብ ሚስብ ቦታ እይታዋ ውስጥ ገባ፡፡
ጀግናዬ እዛ ቦታ አረፍ ብንል ምን ይመስልሀል? ስትለው ከፍታውን እየቀነሰ ወደጎን እየተጎዘ ሄደና 20 የሚሆኑ ዝሆኖች ጀርባ ላይ ቁጭ አደረጋት ከጀርባዋ ተገንጥሎ ተለየና በራሱ መብረር ጀመረ .ደነገጠች.እሱ ከጭንቅላቷ በላይ በአምስት ሜትር እርቀት እየዞራት ነው፡፡ዝሆኑ እላዩ ላይ ዝንብ ያረፈበትም ሳይመስል ተረጋግቶ ከመሰሎቹ ጋር ወደፊት ጎምለል ጎምለል እያለ ይጓዛል…እሷ መረጋጋት አልቻለችም.. ዘላ እንዳትወርድ ከግራም ሆነ ከቀኝ መአት ዝሆኖች ናቸው ያሉት መሬት አርፋ ተስተካክላ ከመቆሞ በፊት በግዙፈ እግሮቻቸው ሚጨፈልቋት መስሎ ተሰማት...እራሷን በጣም ግዙፍና የሰማይ ስባሪ አድርጋ ትቆጥር ነበር.አሁን ከከበቧት ዝሆኖች ጋር እራሷን ስታነፃፅር ግን በዳዴ ሚሄድ ህጸን ልጅ የሆነች መስሎ ተሰማት፡፡
‹‹ጀግናዬ ና አንሳኝ ብዬሀለው. ና››
ንሰሯ ላይ ጮኸችበት …እየተመዘገዘገ ወደእሷ መጠና ትከሻዋን በክንፎቹ ቸብ አድርጎት መልሶ ወደላይ ተነሳ
‹‹አንተ ጫወታ ነው እንዴ የያዝከው ?ስወድህ….?የእኔ ጀግና በእኔ ትጨክናለህ….አላሳዝንህም››ተለማመጠችው፡፡
መልሶ ተከርብቶ መጣና ማጅራቷን ይዞ ወደ ላይ ተነሳና ከዝሆኖቹ መንጋ 20 ሜትር ያህል ራቅ አድርጎ ለምለም ሳር መካከል ቁጭ አደረጋት፡፡ግራና ቀኝ ትከሻዋ ላይ ያለውን ሻንጣዋንና አገልግሏን ከላዮ ላይ አውልቃ ጥላ በጀርባዋ ተዘረረች…ወደ ውስጧና ወደውጭ ደጋግማ አየር እየሰባች ወደውጭ በመልቀቅ ውስጧ በንፅህ አየር ብቻ ሳይሆን መረጋጋትም እንዲነግስባት መሞከር ጀመረች…ንስሯ ከጎኗ መጥቶ ተረጋግጦ ተቀመጠ
ለመረገጋጋት 10 ደቂቃ ያህል ከወሰደች በኃላ
አሁን ያረፉት መርሳቤት ብሄራዊ ፓርክ ነው፡፡ፓርኩ ከናይሮቢ 540ሜትር በስተሰሜን አርቆ ሚገኝ አጠቃላይ ስፋቱ 600 ሜ.እስኬር ስፋት ያለው በመርሳቤት ተራራ ማሀከል አድርጎ በሰሜን ኬንያ የሚገኘው ድንቅ ቦታ ኬድሮንና ንስሯ ከዚህ በፊትም አዘውትረው የሚጎበኙት በጣም ተመራጭ ስፍራቸው ነበር.ይህ ከእኛው ሞያሌ በቅርብ እርቀት ላይ የሚገኘው ፓርክ በልዩ ተፈጥሮ የበለፀገ ስፍራ ነው፤፤ቦታው በጥቅጥቅ ደን የተሸፈነ፤ 3 ሀይቆች ያሉት በተለይ ወፎችን በተመለከተ መነኸሪያቸው ነው ማለት ይቻላል.. ብዛታቸው የማይቆጠር ቀለምና አይነታቸው አስደማሚ ብቻ ሳይሆን ልብንም ስልብ የሚያደርግ ነው፤ከወፎች ቀጥሎ ዝሆኖች በብዛትና በምቾት የሚንጎማለሉበት ስፍራ ነው፡:
ልክ ስምንት ሰዓት ሲሆን አካባቢውን ለቀው ወደ ደቡብ ኬንያ ጉዞቸውን ቀጠሉ…የሚገኙበት በሌላ ጎን በአፍሪካም ሆነ በሀገረ ታንዛኒያ ሁለተኛው ረጅሙ ተራራ ከባህር ጠል በላይ 4566 ኪ.ሜት የሚረዝመው ሜሩ ብለው ሚጠሩት ተራራ የሚገኝበት የሚንዠቀዠቁ ያዶትን እና ዋቤ ሸበሌን መሰል ወንዞች የሚገኙበት የተፈጥሮ ገፀበረከት ቢፌ የሆነ ቦታ ነው ግን በመጠን ብዙም ሰፊ ያለሆነ አርሻ የሚባል ብሄራዊ ፓርክ ነው ከዛ ድንገት ኪሊ ማጀሮ ተራራ ትዝ አላት
አካባቢውን እስኪበቃቸው ከጎበኙና በኃላ ንስሯ እስከፈለገው ጥግ ያለማቆርጥ የመጓዝ ችግር ባይኖርባትም እሷ ከድካሟ የተነሳ ሰውነቷ ስለዛለ ከዛ በላይ መጓዝ አልፈለግችም..በአካባቢው ቅርብ ወደአለ ከተማ ሔደው ማደር ቢችሉም ግን ደግሞ በተለየ ለንስሯ ደህንነት አሳሳቢ ከመሆኑም በተጨማሪ ለእሷ ለራሷም ወደሰው ሀገር ለመግባት የሚያስችል ምንም አይነት ቢዛም ሆነ ፍቃድ ስሌላት እንደዛ ማድረግ አልመረጠች፣
‹‹ጀግናዬ እዚሁ ነው የምናድረው… ዞር ዞር ብለህ እራትህ ፈልግና ና.. እኔ የእናቴን ጩኮ በዚህች ምንጭ ውሀ እያወራረድኩ እበላለሁ›› አለችው…ትዕዛዟን አክብሮ በረረ …እሷም በያዘችው ኮዳ እየተንኳለለ ከሚወርደው የምንጭ ውሀ ቀዳችና በአካባቢው ከሚገኝ ግዙፍ ዛፍ ስር ተጠግታ አረፍ በማለት አገልግሏን ከፈተች…ውስጡ በባለው ማንኪያ እየቆረሰች በቂቤ ተነክሮ የተሰረራውን የእናቷን ተወዳጅ ምግብ በደስታ እያጣጠመች በልታ..ሳትጨርስ ንስሯ የራሱን ግዳይ በመንቁሩ አንገቱን አንቆ ይዞ መጣና ሰሯ አረፈ …ከዛ መሞቱን ካረጋገጠ እየዘነጣጠለ እስፈሪ በሆነ መንገድ መብላት ጀመረ
‹‹አረ ቀስ በል…..የት ትሄዳለህ?››አለችው፡፡
✨ይቀጥላል✨
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹የግድ እኮ ወንድ ጓደኛህ መሆን የለበትም፤ሴትም ጓደኛህ ልትሆን ትችላለች...የመጨረሻ አንድ ማሳሰቢያ ሞባይል ስልኬን በመከታተል ጊዜ እዳታጠፋ...የተመዘገበው በእኔ ስም ሳይሆን እኔም በማላውቀው በሌላ ሰው ስም ነው፡፡አረብ አገር በሄደ ሰው ስም፡፡ለማንኛውም ቻው፡፡ ዝርዝር ህጎችን ቀኑን ስትወስን እንነጋገራለን፡፡ >> ሰልኩ ተዘጋ፡፡
ቀኑ አርብ ነው፡፡ የመጀመሪያ ዕድሉን የሚሞክርበት ቀን ነው፡፡ ቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ የእሬቻ በዓል የሚከበርበት ቦታ ላይ ከትንግርት ጋር ቆሞ በተመስጦ ይቃኛል፡፡ ከትንግርት ጋር ሊመጣ የቻለበት ምክንያት አካባቢውን የሚያውቅና ብቸኝነቱን የሚጋራው ሠው ይዞ እንዲመጣ ከምስጢር ጋር በተነጋገሩበት መሠረት ነው፡፡ከጓደኞቹ መካከል ደግሞ ቢሾፍቱን በጥሩ ሁኔታ የሚያውቃት ሰው አልተገኘም.… ከትንግርት በስተቀር፡፡
በመጀመሪያ ሁኔታውን ሲነግራትና አብራው እንድትሄድ ሲጠይቃት በመገረምና ብስጭት በተቀላቀለበት ስሜት አንገራግራበት ነበር፡፡ በኋላ ግን ተስማምታ እንሆ በዚህ ሠዓት ከጎኑ ትገኛለች፡፡
አሁን የሚገኙት ቢሾፍቱ ከተማ የኦሮሞ ማህበረሠብ ባህላዊ እምነት ማለት የኢሬቻ በዓል በሚከበርበት በሆራ ሀይቅ አካባቢ
ነው፡፡ እምነቱ በዓመት አንድ ጊዜ በታላቅ ክብረ በዓል በመስከረም ወር ከመስቀል ቀጥሎ ባለው እሁድ ቀን ይከበራል፡፡ ከተወሠኑ ዓመታት ወዲህ የእምነቱ ተከታዮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ቱሪስቶች የበዓሉ ተካፋይ እየሆኑ ስለመጡና መንግስትም ቱኩረት ስለሰጠው የታዳሚዎች ቁጥር በሚሊዬኖች ሆኗል ፡፡ ይህም ቁጥር ከዓመት ዓመት ዕድገት እያሳየ ነው ፡
በተጨማሪም በዚህ ቦታ በግለሠብና በግሩፕ በመሆን የተለያየ አምልኮ ስርዓቶችን ይከናወኑበታል፡፡ አካባቢው በትላልቅ ዛፎች የተከበበ ነው፡፡ከረጅም ጉብኝት በኋላ አካባቢውን ለቀው የመጀመሪያ ዕድሉን ለመሞከር ከምስጢር ጋር ወደ ተቀጣጠሩበት በቅርብ እርቀት ላይ ወደሚገኘው መኰንኖች ቁጥር ሁለት ሆቴል ሄዱ፡፡መኰንኖች ደርሠው ወንበር ይዘው ሲቀመጡ አስር ሠዓት ሊሆን አስራ አምስት ደቂቃ ነበር የሚቀረው፡፡
የሆቴሉ አፀድ ሆራ ሀይቅንና ዙሪያውን የከበቡትን ተራሮች በጽሞና ለማየት እንዲያመች ተደርጎ ነው የታነፀው፡፡ የተስተናጋጆች መቀመጫ በሦስት ደረጃ የተከፈለ ነው፡፡ከሦስቱ ደረጃዎች በተጨማሪ ሀይቁን ተጠግቶ ለመቃኘትና ፎቶዎችን ለመነሳት ሃያ አራት የሚሆኑ ደረጃዎችን ወደ ታች ተንደርድረው ከጨረሱ በኋላ እንደ መድረክ ሀይቁ ላይ በብረት ወለል የተሠራ ዙሪያውን 1.5 ሜትር ቁመት ባላቸው ነጭ ቀለም ተቀብቶ በተለያዩ ዲዛይን ባላቸው ባለብረት መከለያ ዘንጎች ተከልሏል፡ ደረጃው አካባቢ ዕድሜ ጠገብ የሚመስል ትልቅ የሾላ ዛፍ አካባቢውን በጥላ አልብሶት ልዩ ድባብ ፈጥሮበታል፡፡ ግቢው ዙሪያውን ግራና ቀኝ በተለያዩ ትላልቅና መካከለኛ መጠን ባላቸው አረንጓዴ ዛፎች የተሞላ ነው፡፡ ግቢው ብቻ ሳይሆን ሀይቁ ዙሪያውን የተደረደሩት ተራሮች አረንጓዴ የለበሱ ስለሆነ ከሀይቁ ጋር በማበር ልብን ስልብ ያደርጋሉ፡፡ሁሴንና ትንግርት
ሁሉንም ነገር በግልፅ ለማየት እንዲያመቻቸው ከላይ ነው የተቀመጡት፡፡
አስተናጋጁ መጣና ‹‹ምን ልታዘዝ?›› አላቸው፡፡
ሁሴን ስፕራይት ሲያዝ ትንግርት ቢራ አዘዘች፡፡
‹‹ምነው ስፕራይት...ጠጪ አይደለሁም ብለህ ዋሽተሀታል እንዴ?›› የአሽሙር ንግግር አሠማች፡፡
በመጠኑ ፈገግ አለ <<ባክሽ በደመነፍስ ነው ያዘዝኩት፤ችግሬ መች የመጠጥ አይነት ሆነና::>>
‹‹አሁን ካሉት ሠዎች እሷን የሚመስል ሠው አላጋጠመህም?››
‹‹ቆይ እስቲ አታጣድፊኝ፤ እያየሁ ነው፡፡ ለነገሩ ሠዓቱም አስር ደቂቃ ይቀረዋል፡፡›› በማለት አይኖቹን እነሱ በተቀመጡበት መስመር ወደ ኋላው አዙሮ አየ፡፡ ሴት የሚባል የለም፡፡ አንድ ስልሳ ዓመት የሚጠጋቸው ሽበታም ጥቁር ሠውዬ ቢራቸውን ከፊት ለፊታቸው አስቀምጠው ሲጋራቸውን ያቦናሉ፡፡
በቀኝ በኩል ዞሮ ተመለከተ፡፡ሁለት ወንበሮች የተያዙ አሉ፡፡ አንዱ ወንበር በሁለት ጎልማሳ ሲያዝ ሌላኛው በሁለት ጥንዶች ተይዞል፡፡ ዓይኖቹን ወደ ታች ላከ ወደ ሁለተኛው ዝቅታ ላይ ወደሚገኙት ተስተናጋጆች ሦስት ሴቶች የሚዝናኑበት ወንበር ከስድስት በላይ ወንድና ሴት የውጭ ዜጎች የተቀመጡበት ጠረጴዛም ታየው፡፡ ዳር ላይ አንድ ብቻዋን የተቀመጠች ሴት ሲያይ ልቡ ብትን አለበት፡፡ ዕድሜዋ በግምት ወደ ሠላሳ ይጠጋል፤ጠይም ነች፤ቆንጆም አስቀያሚም የምትባል አይደለችም፤ ጠረጴዛዋ ባዶውን ነው፤ ሞባይሏ ላይ አፍጥጣ ትጐረጉራለች፡፡
ምልከታውን ለሀይቁ ቅርብ ወደሆነው ሦስተኛው ዝቅታ አሸጋገረ፡፡ አብዛኞቹ ፍቅረኞች የሚመስሉ ጥንዶችና ነጠላ ወንዶች ይበዙበታል፡፡ ሀይቁ ላይ የተሠተረው መድረክም ባዶ ነው፡፡ ዓይኖቹን ወዳለበት
ሲመልስ ያዘዙት መጠጥ ቀርቧል፡፡ ትንግርት በአትኩሮት እያስተዋለችው መጎንጨት ጀምራለች፡፡ እሱም ፊት ለፊቱ ተከፍቶ የተቀመጠለትን ስፕራይት አነሳና አንዴ ገርገጭ በማድረግ ሊደርቅ የፈለገውን ጉሮሮውን አረጠበበት ፤ መልሶ አስቀምጦ ወደ ግራው ዞር ሲል ቅድም ያልነበረች አርባ አመት የሚዘላት አጭር ወፍራም ደማቅ ቀይ ሴት ከሽማግሌው ቀጥሎ ባለው ጠረጴዛ ላይ ተቀምጣ አያት፡፡
‹‹እንዴት ነው?›› አለችው ትንግርት፡፡
‹‹እኔ እንጃ፤እስካሁን ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው እዚህ ግቢ ውስጥ የሚታዩት፡፡››
‹‹የቷ እና የቷ?››
‹‹አንደኛዋ በስተግራችን ከሽማግሌው ቀጥሎ የተቀመጠችው፡፡››
ዞር ብላ አየችና ‹‹እሺ ትንሽ አሮጊት ትመስላለች፡፡››
<<ሁለተኛዋስ?>>
‹‹ሁለተኛዋ ትታይሻለች? እዛ ... >> ንግግሩን አልጨረሰም፡፡
«እዛ የት..?>>
‹‹ተይው በቃ አሁን ደግሞ ብቻዋን አይደለችም፤የሆነ ወንድ መጥቶላታል፡፡››
ከት ብላ ሳቀችና ‹‹ቆይ ግን ብቻዬን ነው የምመጣው ብላ ነግራሀለች?››
‹‹ታዲያ ከማን ጋር ትመጣለች?››
‹‹ለምሳሌ ከሴት ጓደኛዋ ጋር .. ወይም ልክ አንተ እኔን ይዘህ እንደመጣህ ፤ እሷም አንድ የድሮ ወንድ ጓደኛዋን ...>>
<የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል› አለ ያገሬ ሠው፡፡ እንደዛ ከሆነማ ጉድ ፈላብህ በይኝ፡፡ ምን አልባት ከሴት ጓደኛዋ ጋር ልትመጣ ትችል ይሆናል፤ከወንድ ጓደኛዋ ጋር ግን አታደርገውም፤ምክንያቱም አንድ ከወንድ ጋር ያለች ሴት እሷ መስላኝ በስህተት አበባ ባስታቅፋት እንዴት አይነት ችግር ውስጥ እንደምገባ መረዳት አያቅታትም፡፡››
‹‹ይሁንልህ፤እስቲ ቀስ ብለህ እያት ይህቺ ቦርጫሟ፡፡ ዝም ብላ ታይሀለች፤አይኖቿን በሽማግሌው አሻግራ እዚህ ነው የተከለቻቸው፡፡››
‹‹እየቀለድሽ ነው አይደል? .. ብሎ አይኑን ወደ ተባለችው ሴት ሲልክ እውነትም ዓይን ለዓይን
‹‹እውነትም አንቺ .. ይህቺ ግን አትሆንም››
‹‹እንዴት አትሆንም ..?››
‹‹እንደዛ አይነት ማራኪ ድምፅማ ከዚህች ወፍራም ሴት አይወጣም፡፡››
‹‹ባክህ እራስህን አትደልል፤ስንት ከዚህች እጥፍ የሚሠፉ ግን ደግሞ ልብን የሚሠልብ
ድምፅና ያነጋገር ለዛ የታደላቸው ብዙ ሠዎች እኔም አንተም እናውቃለን፡፡››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
‹‹የግድ እኮ ወንድ ጓደኛህ መሆን የለበትም፤ሴትም ጓደኛህ ልትሆን ትችላለች...የመጨረሻ አንድ ማሳሰቢያ ሞባይል ስልኬን በመከታተል ጊዜ እዳታጠፋ...የተመዘገበው በእኔ ስም ሳይሆን እኔም በማላውቀው በሌላ ሰው ስም ነው፡፡አረብ አገር በሄደ ሰው ስም፡፡ለማንኛውም ቻው፡፡ ዝርዝር ህጎችን ቀኑን ስትወስን እንነጋገራለን፡፡ >> ሰልኩ ተዘጋ፡፡
ቀኑ አርብ ነው፡፡ የመጀመሪያ ዕድሉን የሚሞክርበት ቀን ነው፡፡ ቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ የእሬቻ በዓል የሚከበርበት ቦታ ላይ ከትንግርት ጋር ቆሞ በተመስጦ ይቃኛል፡፡ ከትንግርት ጋር ሊመጣ የቻለበት ምክንያት አካባቢውን የሚያውቅና ብቸኝነቱን የሚጋራው ሠው ይዞ እንዲመጣ ከምስጢር ጋር በተነጋገሩበት መሠረት ነው፡፡ከጓደኞቹ መካከል ደግሞ ቢሾፍቱን በጥሩ ሁኔታ የሚያውቃት ሰው አልተገኘም.… ከትንግርት በስተቀር፡፡
በመጀመሪያ ሁኔታውን ሲነግራትና አብራው እንድትሄድ ሲጠይቃት በመገረምና ብስጭት በተቀላቀለበት ስሜት አንገራግራበት ነበር፡፡ በኋላ ግን ተስማምታ እንሆ በዚህ ሠዓት ከጎኑ ትገኛለች፡፡
አሁን የሚገኙት ቢሾፍቱ ከተማ የኦሮሞ ማህበረሠብ ባህላዊ እምነት ማለት የኢሬቻ በዓል በሚከበርበት በሆራ ሀይቅ አካባቢ
ነው፡፡ እምነቱ በዓመት አንድ ጊዜ በታላቅ ክብረ በዓል በመስከረም ወር ከመስቀል ቀጥሎ ባለው እሁድ ቀን ይከበራል፡፡ ከተወሠኑ ዓመታት ወዲህ የእምነቱ ተከታዮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ቱሪስቶች የበዓሉ ተካፋይ እየሆኑ ስለመጡና መንግስትም ቱኩረት ስለሰጠው የታዳሚዎች ቁጥር በሚሊዬኖች ሆኗል ፡፡ ይህም ቁጥር ከዓመት ዓመት ዕድገት እያሳየ ነው ፡
በተጨማሪም በዚህ ቦታ በግለሠብና በግሩፕ በመሆን የተለያየ አምልኮ ስርዓቶችን ይከናወኑበታል፡፡ አካባቢው በትላልቅ ዛፎች የተከበበ ነው፡፡ከረጅም ጉብኝት በኋላ አካባቢውን ለቀው የመጀመሪያ ዕድሉን ለመሞከር ከምስጢር ጋር ወደ ተቀጣጠሩበት በቅርብ እርቀት ላይ ወደሚገኘው መኰንኖች ቁጥር ሁለት ሆቴል ሄዱ፡፡መኰንኖች ደርሠው ወንበር ይዘው ሲቀመጡ አስር ሠዓት ሊሆን አስራ አምስት ደቂቃ ነበር የሚቀረው፡፡
የሆቴሉ አፀድ ሆራ ሀይቅንና ዙሪያውን የከበቡትን ተራሮች በጽሞና ለማየት እንዲያመች ተደርጎ ነው የታነፀው፡፡ የተስተናጋጆች መቀመጫ በሦስት ደረጃ የተከፈለ ነው፡፡ከሦስቱ ደረጃዎች በተጨማሪ ሀይቁን ተጠግቶ ለመቃኘትና ፎቶዎችን ለመነሳት ሃያ አራት የሚሆኑ ደረጃዎችን ወደ ታች ተንደርድረው ከጨረሱ በኋላ እንደ መድረክ ሀይቁ ላይ በብረት ወለል የተሠራ ዙሪያውን 1.5 ሜትር ቁመት ባላቸው ነጭ ቀለም ተቀብቶ በተለያዩ ዲዛይን ባላቸው ባለብረት መከለያ ዘንጎች ተከልሏል፡ ደረጃው አካባቢ ዕድሜ ጠገብ የሚመስል ትልቅ የሾላ ዛፍ አካባቢውን በጥላ አልብሶት ልዩ ድባብ ፈጥሮበታል፡፡ ግቢው ዙሪያውን ግራና ቀኝ በተለያዩ ትላልቅና መካከለኛ መጠን ባላቸው አረንጓዴ ዛፎች የተሞላ ነው፡፡ ግቢው ብቻ ሳይሆን ሀይቁ ዙሪያውን የተደረደሩት ተራሮች አረንጓዴ የለበሱ ስለሆነ ከሀይቁ ጋር በማበር ልብን ስልብ ያደርጋሉ፡፡ሁሴንና ትንግርት
ሁሉንም ነገር በግልፅ ለማየት እንዲያመቻቸው ከላይ ነው የተቀመጡት፡፡
አስተናጋጁ መጣና ‹‹ምን ልታዘዝ?›› አላቸው፡፡
ሁሴን ስፕራይት ሲያዝ ትንግርት ቢራ አዘዘች፡፡
‹‹ምነው ስፕራይት...ጠጪ አይደለሁም ብለህ ዋሽተሀታል እንዴ?›› የአሽሙር ንግግር አሠማች፡፡
በመጠኑ ፈገግ አለ <<ባክሽ በደመነፍስ ነው ያዘዝኩት፤ችግሬ መች የመጠጥ አይነት ሆነና::>>
‹‹አሁን ካሉት ሠዎች እሷን የሚመስል ሠው አላጋጠመህም?››
‹‹ቆይ እስቲ አታጣድፊኝ፤ እያየሁ ነው፡፡ ለነገሩ ሠዓቱም አስር ደቂቃ ይቀረዋል፡፡›› በማለት አይኖቹን እነሱ በተቀመጡበት መስመር ወደ ኋላው አዙሮ አየ፡፡ ሴት የሚባል የለም፡፡ አንድ ስልሳ ዓመት የሚጠጋቸው ሽበታም ጥቁር ሠውዬ ቢራቸውን ከፊት ለፊታቸው አስቀምጠው ሲጋራቸውን ያቦናሉ፡፡
በቀኝ በኩል ዞሮ ተመለከተ፡፡ሁለት ወንበሮች የተያዙ አሉ፡፡ አንዱ ወንበር በሁለት ጎልማሳ ሲያዝ ሌላኛው በሁለት ጥንዶች ተይዞል፡፡ ዓይኖቹን ወደ ታች ላከ ወደ ሁለተኛው ዝቅታ ላይ ወደሚገኙት ተስተናጋጆች ሦስት ሴቶች የሚዝናኑበት ወንበር ከስድስት በላይ ወንድና ሴት የውጭ ዜጎች የተቀመጡበት ጠረጴዛም ታየው፡፡ ዳር ላይ አንድ ብቻዋን የተቀመጠች ሴት ሲያይ ልቡ ብትን አለበት፡፡ ዕድሜዋ በግምት ወደ ሠላሳ ይጠጋል፤ጠይም ነች፤ቆንጆም አስቀያሚም የምትባል አይደለችም፤ ጠረጴዛዋ ባዶውን ነው፤ ሞባይሏ ላይ አፍጥጣ ትጐረጉራለች፡፡
ምልከታውን ለሀይቁ ቅርብ ወደሆነው ሦስተኛው ዝቅታ አሸጋገረ፡፡ አብዛኞቹ ፍቅረኞች የሚመስሉ ጥንዶችና ነጠላ ወንዶች ይበዙበታል፡፡ ሀይቁ ላይ የተሠተረው መድረክም ባዶ ነው፡፡ ዓይኖቹን ወዳለበት
ሲመልስ ያዘዙት መጠጥ ቀርቧል፡፡ ትንግርት በአትኩሮት እያስተዋለችው መጎንጨት ጀምራለች፡፡ እሱም ፊት ለፊቱ ተከፍቶ የተቀመጠለትን ስፕራይት አነሳና አንዴ ገርገጭ በማድረግ ሊደርቅ የፈለገውን ጉሮሮውን አረጠበበት ፤ መልሶ አስቀምጦ ወደ ግራው ዞር ሲል ቅድም ያልነበረች አርባ አመት የሚዘላት አጭር ወፍራም ደማቅ ቀይ ሴት ከሽማግሌው ቀጥሎ ባለው ጠረጴዛ ላይ ተቀምጣ አያት፡፡
‹‹እንዴት ነው?›› አለችው ትንግርት፡፡
‹‹እኔ እንጃ፤እስካሁን ሁለት ሴቶች ብቻ ናቸው እዚህ ግቢ ውስጥ የሚታዩት፡፡››
‹‹የቷ እና የቷ?››
‹‹አንደኛዋ በስተግራችን ከሽማግሌው ቀጥሎ የተቀመጠችው፡፡››
ዞር ብላ አየችና ‹‹እሺ ትንሽ አሮጊት ትመስላለች፡፡››
<<ሁለተኛዋስ?>>
‹‹ሁለተኛዋ ትታይሻለች? እዛ ... >> ንግግሩን አልጨረሰም፡፡
«እዛ የት..?>>
‹‹ተይው በቃ አሁን ደግሞ ብቻዋን አይደለችም፤የሆነ ወንድ መጥቶላታል፡፡››
ከት ብላ ሳቀችና ‹‹ቆይ ግን ብቻዬን ነው የምመጣው ብላ ነግራሀለች?››
‹‹ታዲያ ከማን ጋር ትመጣለች?››
‹‹ለምሳሌ ከሴት ጓደኛዋ ጋር .. ወይም ልክ አንተ እኔን ይዘህ እንደመጣህ ፤ እሷም አንድ የድሮ ወንድ ጓደኛዋን ...>>
<የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል› አለ ያገሬ ሠው፡፡ እንደዛ ከሆነማ ጉድ ፈላብህ በይኝ፡፡ ምን አልባት ከሴት ጓደኛዋ ጋር ልትመጣ ትችል ይሆናል፤ከወንድ ጓደኛዋ ጋር ግን አታደርገውም፤ምክንያቱም አንድ ከወንድ ጋር ያለች ሴት እሷ መስላኝ በስህተት አበባ ባስታቅፋት እንዴት አይነት ችግር ውስጥ እንደምገባ መረዳት አያቅታትም፡፡››
‹‹ይሁንልህ፤እስቲ ቀስ ብለህ እያት ይህቺ ቦርጫሟ፡፡ ዝም ብላ ታይሀለች፤አይኖቿን በሽማግሌው አሻግራ እዚህ ነው የተከለቻቸው፡፡››
‹‹እየቀለድሽ ነው አይደል? .. ብሎ አይኑን ወደ ተባለችው ሴት ሲልክ እውነትም ዓይን ለዓይን
‹‹እውነትም አንቺ .. ይህቺ ግን አትሆንም››
‹‹እንዴት አትሆንም ..?››
‹‹እንደዛ አይነት ማራኪ ድምፅማ ከዚህች ወፍራም ሴት አይወጣም፡፡››
‹‹ባክህ እራስህን አትደልል፤ስንት ከዚህች እጥፍ የሚሠፉ ግን ደግሞ ልብን የሚሠልብ
ድምፅና ያነጋገር ለዛ የታደላቸው ብዙ ሠዎች እኔም አንተም እናውቃለን፡፡››
‹‹እሱስ ትክክል ነሽ›
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሳባ የአሰላን ከተማ ለቃ እንደወጣች በደመነፍስ ነበር ስትነዳ የነበረው፡፡ ሀሳቧ ሁሉ ወደኃላ ተመልሷል..ያንን የተረገመ ስራ እንዴት እንደ ጀመረች አስር አመት ወደኃላ ተመልሳ ማብላላት ጀመረች፡፡
ከ10 ዓመት በፊት
ያኔ በዛ ዘመን አዲሱን ስራዋን ለመጀመር ከሰገን ጋር የመጨረሻ ድርድር ስታደርግ እና ሲለያዩ አንድ ምክር ሰጥታት ነበር…‹‹ድንግል ከሆንሽ ለምትወጂው ሰው ስጪው፡፡››ነበር ያለቻት…ግን በፍጥነት ማድረግ አልቻለችም ነበር…በወቅቱ የምትወደው ሰው ልቧን ሰብሮ ካሳዘናት ሰነባብቷል….‹‹ለእሱ ድንግልና ሳይሆን ከተቻለ በቀል ነው የሚገባው››ስትል በማሰብ….ስለድንግልናዋ ማሰብና መጨነቅ ትታ…ዕቃዋን በየካርቶኑ እያስገበባች አሸገች፤ልብሶቿን በሁለት ሻንጣ ጠቅጥቃ አሳሰረች…የምትተኛበት ፍራሽ ብቻ እንደተዘረጋ ቀረ…ቀጥሎ ምን እንደምታደርግ ግራ ገባት፡፡መቼስ ይሄን ሁሉ ኮተት ይዛ በህዝብ ትራንስፖርት ተጠቅማ አሰላ ድረስ ማጓጓዝ አትችልም...እንዴት አድርጋ…‹‹ደግሞ ስኖርበት ባዶ የነበረው ቤት አሁን ልለቅ ስል እንዴት ነው እንዲህ ሜዳውን የሞላው?››ሥትል በማሰብ ተገረመች፡፡‹‹ግን አሁን ይሄንን ሁሉ ኮተት ብረት ድስት፤ሰሀን፤ብርጭቆ ምድጃ ለምንድነው የሰበሰብኩት? ለምን ለተቸገረ አላከፋፍለውም?››ራሷን በትዝብት ጠየቀች፡፡
ግን ደፍራ ነገ ሀብታምና ሁሉ ነገር የተረፈው እንደምትሆን ተማምና ‹‹አይ ይሄን ኮልኮሌ አልፈልግም ላከፋፍለው››ልትል አልቻለችም…
ወሰነች.‹‹አዎ ብር አለኝ… አሰላ ድረስ የሚወስድልኝ መኪና ብፈልግ ይሻላል››ስትል አሰበች…‹‹አዎ መርካቶ ብሄድ ጭነት መኪና አላጣም….ጭነው ሲጨርሱ በዚሁ ጎራ ቢሉ ከላይ ጣል ጣል አድርገው ይወስዱልኛል….››ብላ ስሌት ሰራችና ወደመርካቶ ለመሄድ ካሰበች በኃላ ሌላ የተሻለ ያለችው ሀሳብ ብልጭ አለላት፡
ደምሳሽ ትዝ ኣላት….እርግጥ በወቅቱ ለዚህ የሚያበቃ ትውውቅም ሆነ ንግግር.አልነበራቸውም...ቢሆንም.ያው‹‹ቤተሰብ ሆነናል››ብሏት የለ. ብትጠይቀው ምንም ክፋት እንደሌለው አሰላች…ሸፌር ስለሆነ ሌሎች ሹፌሮችን ስለሚያውቅ ወደአሰላ የሚሄድ የጭነት መኪና ብዙም ሳይለፋ በስልክ ሊጨርስላት ይችላል…ስልኳን አወጣችና ደወለችለት..ከሶስት ጥሪ በኋላ ተነሳ..
‹‹ጤና ይስጥልኝ የእኔ እመቤት››
‹‹አቶ ደምሳሽ ሳባ ነኝ .አወቅከኝ?በቀደም…››
‹‹እመቤቴ አውቄሻለሁ..ማብራራት አይጠበቅብሽም…አንቺን እንዴት ልዘነጋ እችላለሁ፡፡ለዛውም ቤተሰብ ሆነን?››ነበር ያላት…
‹‹በእውነት ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ነው ያደረከው››አለችው ከምሯ፡፡
‹‹አረ ምንም የተለየ ነገር አልተናገርኩም…ለማንኛውም ምን ልታዘዝ?››
‹‹እየፈራሁ ነው የደወልኩት..ሌላ ላስቸግረው የምችል ሰው ስለሌለ ነው እባክህ ከድፍረት አትቁጠርብኝ››
‹‹በነገራችን ላይ አልተነገረሽም መሰለኝ?››
‹‹ምኑን?››
‹‹ከዛሬ ጀምሬ በማንኛውም ነገር አንቺን እንድጠብቅ፤እንድታዘዝና የምትፈልጊውን ነገር ሁሉ እንዳሟላልሽ ታዝዣለሁ…ስለዚህ እኔን ማዘዙን ከዛሬው ተለማመጂው…ለአንቺ መታዘዝ ስራዬ ነው›› አላት፡፡
‹‹ማዘዙን?››
‹‹አዎ ማዘዙን››
‹‹አይ እንዳልጠየቅህ አደረከኝ…በቃ ይቅርብኝ ሌላ አማራጭ እፈልጋለሁ፡፡››
‹‹አረ ተይ ቀለል አድርጊውና የምትፈልጊውን ንገሪኝ..ካለበለዚያ አሁኑኑ ሰፈርሸ እመጣለሁ››አላት
‹‹ኸረ ተው…እሺ ያው ሹፌር ስለሆንክ ሹፌሮችን ታውቃለህ ብዬ ነው››
‹‹አዎ በደንብ አውቃለሁ…ምን ፈለግሽ?››
‹‹የፈለኩትማ ያው ሰሞኑን ስልጠና ጠቅልዬ ስለምገባ የምኖርበትን ቤት ለቅቄያለሁ….ቤተሰቦቼ ያሉት አሰላ ነው…እቃዎቼን ወደእዛ ለመውሰድ ፈልጌ ነበር…እና ወደዛ የሚሄድ የጭነት መኪና ፈልጌ ነበር..እንዴት እንደማገኝ ግራ ገብቶኝ ነው››
‹‹ወይ ለዚህች ነው እንዴ..?ለመቼ ነው..?››
‹‹ከተቻለማ ለዛሬ ነው…ካልሆነም ለነገ ጠዋት…››
‹‹ስልኬን ጠብቂ…መልሼ እደውላለሁ፡፡››
‹‹በእውነት ከልቤ ነው የማመሰግነው››
‹‹በይ ቻው በቤተሰቦች መካከል መመሰጋገን የለም ››ብሎ ስልኩን ዘጋ፡፡
ከ8 ደቂቃ በኃላ ነበር ስልኳ መልሶ የጠራው…ስታየው ደምሳሽ ነው..በዚህ ፍጥነት አልጠበቀችም.
አነሳችውና ‹‹ሄሎ አገኘህልኝ?››አለችው፡፡
አዎ እቃሽ ብዙ ነው እንዴ ?ማለት ፒካፕ መኪና አይችለውም..?››
‹‹አረ በደንብ ነው ሚችለው››
‹‹እንግዲያው አሁን 5 ሰዓት ሆኗል 7 ሰዓት ሰፈር ደርሶ ይደውልልሻል..እስከዛ የቀረሽ ነገር ካለ አስተካክይ››
በደስታ ስልኩን ዘጋችና የመጨረሻውን ዝግጅት ማድረግ ጀመረች፡
ለ7 ሩብ ጉዳይ ደወለላት...ፈጥና አነሳችው
‹‹ሄሎ ደምሳሽ...እንዴት ሆነልህ?››
‹‹ያው ግሎባል ጋር ሰማያዊ ደብል ፒካኘ ቲዬታ መኪና ይዞ እየጠበቀሽ ነው።››ስልኳን እያወራች ቤቱን ለቃ ወጣች‹‹እንዴት እንደማመሰግንህ አላውቅም"
"ችግር የለውም… ስትመጪ ምሳ ትጋብዢኛለሽ"
‹‹አረ ችግር የለውም...ግን ክፍያውን እንዴት ነው የማደርገው ማለቴ
ነግሮሀል?"
‹‹ዋጋው ችግር የለውም...ወላጆችሽ ምሳና ቡና ከጋበዙት ይበቃዋል››
‹‹እውነቴን እኮ ነው...ትቀልድብኛለህ አይደል?››
በዚህ ጊዜ ግሎባል ጋር ደርሳ ነበር ...በምልክት የነገራትን ፒካፕ ወዲያው አየቻት...ለሹፌሩ ወደእሷ እንዲመጣ በእጇ ምልክት ጠራችውና መኪናዋን ማንቀሳቀሱን ካየች በኃላ ፊቷን አዙራ ወደቤቷ ተንቀሳቀሰች፡፡
‹‹ሰውዬውን አግኝቼዋለሁ" ‹‹እ..ታዲያ አናገርሽው?" ‹‹አይ አላናገርኩትም"
"ታዲያ ልደውልለትና ልጠይቅልሽ ወይስ አንቺው እዛው ትከራከሪዋለሽ?"
‹‹አይ አመሰግንሀለሁ...ከዚህ በላይማ ላስቸግርህ አልፈልግም...በቃ ቻው።››
‹‹ቻው በቃ ሚቸግርሽ ነገር ካለ ደውይ››
እሷ የቤቷ በራፍ ጋር ስትደርስ ፒካፗ አጠገቧ ደርሳ በስሱ ክላክስ ሲያደርግላት ስልኩን ፈጠን ብላ ዘጋችና ወደግቢ ገብታ የመኪና መግቢያ በራፍ ከፈተች… መኪናዋ ወደውስጥ ዘልቃ ገባችና የግቢው መሀል አካባቢ ቆማ ከገቢናዋ ሹፌሩ ዱብ ብሎ ወረደ...በድንጋጤ እጇን አፏ ላይ ከደነች።
‹‹ምነው አስደነገጥኩሽ እንዴ?››
"እዚህ ሆነህ ነው እንዴ የምታስለፈልፈኝ...?ባለመኪናው የት አለ?"
‹‹መኪናው የድርጅቱ ነው...ሹፌሩም ደግሞ እኔ ነኝ.."
‹‹ኸረ ደምሳሽ እንዲህ እኮ መቸገር አልነበረብህም።አሰላ ድረስ እኮ ነው።
"ይሄ የእኔ ሀሳብ አይደለም..ታዝዤ ነው...መኪና እየፈለግሽ እንደሆነ ለሠገን ስነግራት...ራስህ አድርስላት ብላ አዘዘቺኝ...ይልቅ አሁን ሰዓቱ እየነጎደ ስለሆነ እቃሺን ቶሎ ጫን ጫን አድርገን እንውጣ›› አላት። እየከበዳት እቃዋን ወደ ተቆለለበት ክፍል ይዛው ገባች..እቃውን ጭነው ከግቢው ለመውጣት 20 ደቂቃ ብቻ ነበር የወሰደባቸው።
///
11 ሰዓት ላይ ቤት ደረሱ እቃው እስኪወርድ፤ መክሰስ በልተው የተፈላውን ቡና ጠጥተው እስኪያጠናቅቁ ለአንድ ሰአት ሩብ ጉዳይ ሆነ...ሳባ ከቤተሰቦቿ ጋር ስትጫወት አድራ በማግስቱ ረፈድፈድ ሲል ነበር መመለስ የፈለገችው። ያንን ዕቅድ ያወጣችው ሹፌሩ ደምሳሽ መሆኑን ከማወቋ በፊት ነበር። በኋላ ግን ለእሷ ብሎ አሰላ ድረስ መጥቶ እንዴት ብቻውን እንዲመለስ ትተወው?ያ ነው የጨነቃት፡፡ እርግጥ እርሱም በእንግድነት እነሱ ቤት እንዲያድርና ጥዋት አብረው እንዲመለሡ ጠይቃው ነበር። እሱ በማግስቱ 12 ሰዓት አዲስ አበባ ላይ የሚሰራው ስራ ስላለ እንደማይችል ስለነገራት አብራው ለመመለስ ወሰነች። ሁሉን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሳባ የአሰላን ከተማ ለቃ እንደወጣች በደመነፍስ ነበር ስትነዳ የነበረው፡፡ ሀሳቧ ሁሉ ወደኃላ ተመልሷል..ያንን የተረገመ ስራ እንዴት እንደ ጀመረች አስር አመት ወደኃላ ተመልሳ ማብላላት ጀመረች፡፡
ከ10 ዓመት በፊት
ያኔ በዛ ዘመን አዲሱን ስራዋን ለመጀመር ከሰገን ጋር የመጨረሻ ድርድር ስታደርግ እና ሲለያዩ አንድ ምክር ሰጥታት ነበር…‹‹ድንግል ከሆንሽ ለምትወጂው ሰው ስጪው፡፡››ነበር ያለቻት…ግን በፍጥነት ማድረግ አልቻለችም ነበር…በወቅቱ የምትወደው ሰው ልቧን ሰብሮ ካሳዘናት ሰነባብቷል….‹‹ለእሱ ድንግልና ሳይሆን ከተቻለ በቀል ነው የሚገባው››ስትል በማሰብ….ስለድንግልናዋ ማሰብና መጨነቅ ትታ…ዕቃዋን በየካርቶኑ እያስገበባች አሸገች፤ልብሶቿን በሁለት ሻንጣ ጠቅጥቃ አሳሰረች…የምትተኛበት ፍራሽ ብቻ እንደተዘረጋ ቀረ…ቀጥሎ ምን እንደምታደርግ ግራ ገባት፡፡መቼስ ይሄን ሁሉ ኮተት ይዛ በህዝብ ትራንስፖርት ተጠቅማ አሰላ ድረስ ማጓጓዝ አትችልም...እንዴት አድርጋ…‹‹ደግሞ ስኖርበት ባዶ የነበረው ቤት አሁን ልለቅ ስል እንዴት ነው እንዲህ ሜዳውን የሞላው?››ሥትል በማሰብ ተገረመች፡፡‹‹ግን አሁን ይሄንን ሁሉ ኮተት ብረት ድስት፤ሰሀን፤ብርጭቆ ምድጃ ለምንድነው የሰበሰብኩት? ለምን ለተቸገረ አላከፋፍለውም?››ራሷን በትዝብት ጠየቀች፡፡
ግን ደፍራ ነገ ሀብታምና ሁሉ ነገር የተረፈው እንደምትሆን ተማምና ‹‹አይ ይሄን ኮልኮሌ አልፈልግም ላከፋፍለው››ልትል አልቻለችም…
ወሰነች.‹‹አዎ ብር አለኝ… አሰላ ድረስ የሚወስድልኝ መኪና ብፈልግ ይሻላል››ስትል አሰበች…‹‹አዎ መርካቶ ብሄድ ጭነት መኪና አላጣም….ጭነው ሲጨርሱ በዚሁ ጎራ ቢሉ ከላይ ጣል ጣል አድርገው ይወስዱልኛል….››ብላ ስሌት ሰራችና ወደመርካቶ ለመሄድ ካሰበች በኃላ ሌላ የተሻለ ያለችው ሀሳብ ብልጭ አለላት፡
ደምሳሽ ትዝ ኣላት….እርግጥ በወቅቱ ለዚህ የሚያበቃ ትውውቅም ሆነ ንግግር.አልነበራቸውም...ቢሆንም.ያው‹‹ቤተሰብ ሆነናል››ብሏት የለ. ብትጠይቀው ምንም ክፋት እንደሌለው አሰላች…ሸፌር ስለሆነ ሌሎች ሹፌሮችን ስለሚያውቅ ወደአሰላ የሚሄድ የጭነት መኪና ብዙም ሳይለፋ በስልክ ሊጨርስላት ይችላል…ስልኳን አወጣችና ደወለችለት..ከሶስት ጥሪ በኋላ ተነሳ..
‹‹ጤና ይስጥልኝ የእኔ እመቤት››
‹‹አቶ ደምሳሽ ሳባ ነኝ .አወቅከኝ?በቀደም…››
‹‹እመቤቴ አውቄሻለሁ..ማብራራት አይጠበቅብሽም…አንቺን እንዴት ልዘነጋ እችላለሁ፡፡ለዛውም ቤተሰብ ሆነን?››ነበር ያላት…
‹‹በእውነት ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ነው ያደረከው››አለችው ከምሯ፡፡
‹‹አረ ምንም የተለየ ነገር አልተናገርኩም…ለማንኛውም ምን ልታዘዝ?››
‹‹እየፈራሁ ነው የደወልኩት..ሌላ ላስቸግረው የምችል ሰው ስለሌለ ነው እባክህ ከድፍረት አትቁጠርብኝ››
‹‹በነገራችን ላይ አልተነገረሽም መሰለኝ?››
‹‹ምኑን?››
‹‹ከዛሬ ጀምሬ በማንኛውም ነገር አንቺን እንድጠብቅ፤እንድታዘዝና የምትፈልጊውን ነገር ሁሉ እንዳሟላልሽ ታዝዣለሁ…ስለዚህ እኔን ማዘዙን ከዛሬው ተለማመጂው…ለአንቺ መታዘዝ ስራዬ ነው›› አላት፡፡
‹‹ማዘዙን?››
‹‹አዎ ማዘዙን››
‹‹አይ እንዳልጠየቅህ አደረከኝ…በቃ ይቅርብኝ ሌላ አማራጭ እፈልጋለሁ፡፡››
‹‹አረ ተይ ቀለል አድርጊውና የምትፈልጊውን ንገሪኝ..ካለበለዚያ አሁኑኑ ሰፈርሸ እመጣለሁ››አላት
‹‹ኸረ ተው…እሺ ያው ሹፌር ስለሆንክ ሹፌሮችን ታውቃለህ ብዬ ነው››
‹‹አዎ በደንብ አውቃለሁ…ምን ፈለግሽ?››
‹‹የፈለኩትማ ያው ሰሞኑን ስልጠና ጠቅልዬ ስለምገባ የምኖርበትን ቤት ለቅቄያለሁ….ቤተሰቦቼ ያሉት አሰላ ነው…እቃዎቼን ወደእዛ ለመውሰድ ፈልጌ ነበር…እና ወደዛ የሚሄድ የጭነት መኪና ፈልጌ ነበር..እንዴት እንደማገኝ ግራ ገብቶኝ ነው››
‹‹ወይ ለዚህች ነው እንዴ..?ለመቼ ነው..?››
‹‹ከተቻለማ ለዛሬ ነው…ካልሆነም ለነገ ጠዋት…››
‹‹ስልኬን ጠብቂ…መልሼ እደውላለሁ፡፡››
‹‹በእውነት ከልቤ ነው የማመሰግነው››
‹‹በይ ቻው በቤተሰቦች መካከል መመሰጋገን የለም ››ብሎ ስልኩን ዘጋ፡፡
ከ8 ደቂቃ በኃላ ነበር ስልኳ መልሶ የጠራው…ስታየው ደምሳሽ ነው..በዚህ ፍጥነት አልጠበቀችም.
አነሳችውና ‹‹ሄሎ አገኘህልኝ?››አለችው፡፡
አዎ እቃሽ ብዙ ነው እንዴ ?ማለት ፒካፕ መኪና አይችለውም..?››
‹‹አረ በደንብ ነው ሚችለው››
‹‹እንግዲያው አሁን 5 ሰዓት ሆኗል 7 ሰዓት ሰፈር ደርሶ ይደውልልሻል..እስከዛ የቀረሽ ነገር ካለ አስተካክይ››
በደስታ ስልኩን ዘጋችና የመጨረሻውን ዝግጅት ማድረግ ጀመረች፡
ለ7 ሩብ ጉዳይ ደወለላት...ፈጥና አነሳችው
‹‹ሄሎ ደምሳሽ...እንዴት ሆነልህ?››
‹‹ያው ግሎባል ጋር ሰማያዊ ደብል ፒካኘ ቲዬታ መኪና ይዞ እየጠበቀሽ ነው።››ስልኳን እያወራች ቤቱን ለቃ ወጣች‹‹እንዴት እንደማመሰግንህ አላውቅም"
"ችግር የለውም… ስትመጪ ምሳ ትጋብዢኛለሽ"
‹‹አረ ችግር የለውም...ግን ክፍያውን እንዴት ነው የማደርገው ማለቴ
ነግሮሀል?"
‹‹ዋጋው ችግር የለውም...ወላጆችሽ ምሳና ቡና ከጋበዙት ይበቃዋል››
‹‹እውነቴን እኮ ነው...ትቀልድብኛለህ አይደል?››
በዚህ ጊዜ ግሎባል ጋር ደርሳ ነበር ...በምልክት የነገራትን ፒካፕ ወዲያው አየቻት...ለሹፌሩ ወደእሷ እንዲመጣ በእጇ ምልክት ጠራችውና መኪናዋን ማንቀሳቀሱን ካየች በኃላ ፊቷን አዙራ ወደቤቷ ተንቀሳቀሰች፡፡
‹‹ሰውዬውን አግኝቼዋለሁ" ‹‹እ..ታዲያ አናገርሽው?" ‹‹አይ አላናገርኩትም"
"ታዲያ ልደውልለትና ልጠይቅልሽ ወይስ አንቺው እዛው ትከራከሪዋለሽ?"
‹‹አይ አመሰግንሀለሁ...ከዚህ በላይማ ላስቸግርህ አልፈልግም...በቃ ቻው።››
‹‹ቻው በቃ ሚቸግርሽ ነገር ካለ ደውይ››
እሷ የቤቷ በራፍ ጋር ስትደርስ ፒካፗ አጠገቧ ደርሳ በስሱ ክላክስ ሲያደርግላት ስልኩን ፈጠን ብላ ዘጋችና ወደግቢ ገብታ የመኪና መግቢያ በራፍ ከፈተች… መኪናዋ ወደውስጥ ዘልቃ ገባችና የግቢው መሀል አካባቢ ቆማ ከገቢናዋ ሹፌሩ ዱብ ብሎ ወረደ...በድንጋጤ እጇን አፏ ላይ ከደነች።
‹‹ምነው አስደነገጥኩሽ እንዴ?››
"እዚህ ሆነህ ነው እንዴ የምታስለፈልፈኝ...?ባለመኪናው የት አለ?"
‹‹መኪናው የድርጅቱ ነው...ሹፌሩም ደግሞ እኔ ነኝ.."
‹‹ኸረ ደምሳሽ እንዲህ እኮ መቸገር አልነበረብህም።አሰላ ድረስ እኮ ነው።
"ይሄ የእኔ ሀሳብ አይደለም..ታዝዤ ነው...መኪና እየፈለግሽ እንደሆነ ለሠገን ስነግራት...ራስህ አድርስላት ብላ አዘዘቺኝ...ይልቅ አሁን ሰዓቱ እየነጎደ ስለሆነ እቃሺን ቶሎ ጫን ጫን አድርገን እንውጣ›› አላት። እየከበዳት እቃዋን ወደ ተቆለለበት ክፍል ይዛው ገባች..እቃውን ጭነው ከግቢው ለመውጣት 20 ደቂቃ ብቻ ነበር የወሰደባቸው።
///
11 ሰዓት ላይ ቤት ደረሱ እቃው እስኪወርድ፤ መክሰስ በልተው የተፈላውን ቡና ጠጥተው እስኪያጠናቅቁ ለአንድ ሰአት ሩብ ጉዳይ ሆነ...ሳባ ከቤተሰቦቿ ጋር ስትጫወት አድራ በማግስቱ ረፈድፈድ ሲል ነበር መመለስ የፈለገችው። ያንን ዕቅድ ያወጣችው ሹፌሩ ደምሳሽ መሆኑን ከማወቋ በፊት ነበር። በኋላ ግን ለእሷ ብሎ አሰላ ድረስ መጥቶ እንዴት ብቻውን እንዲመለስ ትተወው?ያ ነው የጨነቃት፡፡ እርግጥ እርሱም በእንግድነት እነሱ ቤት እንዲያድርና ጥዋት አብረው እንዲመለሡ ጠይቃው ነበር። እሱ በማግስቱ 12 ሰዓት አዲስ አበባ ላይ የሚሰራው ስራ ስላለ እንደማይችል ስለነገራት አብራው ለመመለስ ወሰነች። ሁሉን
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ምስራቅ ኮስተር ብላ ‹‹አትልፈስፈስ…ጠንከር ብለህ መሆን ስለሚገባው ነገር ብቻ እንነጋር፡፡››አለችው፡፡
ናኦልም‹‹ምን የሚሆን ነገር አለና እንነጋራለን…በዚህ ምድር ላይ አንድ አለቺኝ የምላት እህቴን እንዲህ ባለ ሁኔታ አጥቼያት እኔስ በህይወት መኖሬን ቀጥላለው?››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹አይዞህ ኑሀሚ እንደዚህ ካሉ ብዙ አደጋዎች ሰርቫይቭ የማድረግ ልምድ ያላት ልጅ ነች፤ደግሞ በምድር ላይ ያለችህ እሷ ብቻ አይደለችም..እኔም እኮ ስላለሁ መሰለኝ አሁን በዚህ የሀዘንህ ወቅት አጠገብህ ያለሁት፡፡
‹‹እሱማ እውነትሽን ነው፡፡››
‹‹እኮ ..በል ተነስና መልስ እንመልስለት፡፡››
ከተዘረፈጠበት ተነሳና ወደእሷ ቀረበ‹‹ምን ብለን?››
‹‹ያልከኸውን አደርጋለው..ለማንም ሳልናገር ያልከው ሀገር ድረስ እመጣለሁ..ግን እህቴ በህይወት መኖሯን በምን አውቃለሁ?አንድ ማረጋገጫ ስጠኝ፡፡››
‹‹አዎ እንደዛ ብንለው ይሻላል አይደል…?ወይ ተጨማሪ ፎቶ ወይ ቪዲዬ ይልክልናል፡፡ወይ ደግሞ በስልክም ሊያገናኘን ይችላል፡፡››
‹‹በቃ ራስሽ ፃፊው››
እንደማሰብ አለችና ፃፈችና ላከች፡፡መልስ እስኪመጣ ለመጠበቅ ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ፡፡ለሁለቱም የሚጠጣ ቢራ አቀረበና እሱን እየጠጡ በትካዜ በስልኩ ከአሁን አሁን የሚላከውን ኢሜል መጠበቅ ቀጠለ፡፡
ከሶስት ሰዓት በኃላ ተጨማሪ ፎቶ ተላከላቸው፡፡እንሱ ያላወቁት እነዛ ፎቶዎች የተመረጡት ከኑሀሚ ስልክ ውስጥ በፔሩ ቆይታዋ በተያዩ ጊዜያቶች ከተነሳቸው ውስጥ የተመረጡትን ነው፡፡
ከፎቶ ጋር አጭር መልዕክት ተልዕኮል
‹‹ባቀረብንልህ ሀሳብ ከተስማማን አሁኑኑ አሳውቀን፡፡››ይላል፡፡
‹‹እ ምን አሰብሽ? ››አለት፡፡ ከምስራቅ የተሻለ ሀሳብ ለማግኘት እየተመኘ ጠየቃት.. ምርጫ የለንም ‹‹ተስማምቼያለሁ ብለህ ላክላቸው፡፡››እንዳለችው አደረገ፡፡
በል የጉዞ ሰነዶችህን አዘጋጅ…በሶስት ቀን ውስጥ አስፈላጊውን ገንዘብ ስለምንልክልህ ሙሉ ስምህን እና አስፈላጊ መረጃዎችን ላክልን፡፡እንደተነጋገርነው ግን ይሄንን ሚስጥር ሌላ ለሶስተኛ ወገን ለመንግስት አሳልፈህ ብትሰጥ ነገሮች ሁሉ ያከትምላቸዋል….ከዛ በኃላ
እህትህን በዚህ ምድር ላይ ዳግመኛ የማግኘት እድልህ ከዜሮ በታች ይሆናል…በል ፍጠን ይላል፡፡
‹‹አነበብሽው አይደል?››
‹‹አዎ ..አነበብኩት..››አለችና ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡
‹‹ምነው? ››
‹‹ልሄድ ነው፡፡››
‹‹ልሄድ ነው በእንደዚህ አይነት በተሰባበርኩበት ሁኔታ ላይ ሆኜ ጥለሺኝ ልትሄጂ ነው….፡፡››
‹‹ጎረምሳው ተረጋጋ እንጂ ..ይልቅ እራስህን ለረጅምና አስቸጋሪ ጉዞ አዘጋጅ፡፡እኔ ሄጄ ለጉዞ አስፈላጊ የሆኑ ፖስፖርትና ቢዛዎችን ላዘጋጅ፡፡ ታውቃለህ እነዚህን የጉዞ ሰነዶች በአሁኑ ጊዜ በስድስት ወር ውስጥም ማግኘት አይቻልም፡፡አኔ ደግሞ ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማግኘት
አለብኝ፡፡ ለዚህ ደግሞ ደቂቃዎችን ሳላባክን ከአሁን ያለኝን ኃይልና መስመር ሁሉ ተጠቅሜ ማሳካት መቻል አለብኝ…እ ምን ትላለህ ጎረምሳው?››
ተንደረደረ ሄደና ተጠመጠመባት፡፡እሷም እጆቾን በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመቻቸው… ጭምቅ አደረጋት፡፡
‹‹አንቺ ስላለሺኝ ሁሌ ደስተኛ ነኝ፡፡ዘላለም በእቅፍሽ ውስጥ መኖር ነው ምኞቴ…በጣም ነው የምወድሽ….››አላት
‹‹….ተራጋጋ፡፡ከዚህ በላይ ከወራን እንባዬ ያመልጠኛል፡፡››አለችና ከእቅፉ ወጥታ ፈዞ በቆመበት ፊቷን አዙራ ወጥታ ሄደች፡፡በቦዘዙ አይኖቹ በስስት እያያት በሀሳቡ ሸኛት፡፡..
///
ከሶስት ቀን በኃላ በአለምአቀፍ የሀዋላ አስተላላፊዎች አማካይነት 50 ሺ ዶላር ተላከለት፡፡ያልጠበቀው ነገር ነበር፡፡ብሩ ሲደርሰው ነገሩ ሲሪዬስ እንደሆነ እሱ ብቻ ሳይሆን ምስራቅም ተገነዘበች፡፡ሁለቱም መመለስ ያቃቸው ይሄ ሁሉ አጋቾቹ ይሄን ሁሉ ኢንቨስትመንትና ጥረት የሚያደርጉት ከእሷ ምን ፈልገው ነው? የሚለውን ነው ፤የእሱንስ ወደፔሩ መሄድ ለምን ፈለጉት?››በተለይ ይሄን ጥያቄ ከአንደበቷ አውጥታ ለእሱ አትንገረው እንጂ ምስራቅንም በጣም ነው ያሳሰባት፡፡
ናኦል ገንዘቡ እንደደረሰው ካወቀ በኃላ እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም፡፡ሰዓቱ ገፍቶ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኖኛል በተኛበት አልጋ ላይ እየተገላበጠ በትዝታ ወደኃላ ወደልጅነታቸው ተጓዘ፡፡ምስራቅ እሱና ተወዳጅ እህቱን ከጎዳና አንስታ እንዴት ሰላይ እዳደረገቻቸው በዝርዝር ትዝ አለው፡፡
ከ15 አመት በፊት ምስራቅ የወንድሜ ቤት ነው ብላ ከጓዳና አንስታ ጎተራ የሚገኝ ኮንደምንዬም ቤት ከወሰደቻቸው በኃላ ከአዛው ቤት ሳይወጡ ሁለት ወር ሙሉ ቆይተው
ነበር፡፡ በሶስተኛው ወር ግን ማታ እራት በልተው ቴሌቬዥን እያዩ እያለ ድንገት ሪሞቱን አንስታ ቴሌቪዝኑን አጠፋችና ፊት ለፊታቸው ቁጭ አለች፡፡
እህትና ወንድም እርስበር ተያዩ ፡፡የሆነ ነገር ልትነግራቸው እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡፡ግን የጠረጠሩት በቃ እስካሬ ለሁለት ወር በምቾትና በድሎት በወንድሜ ቤት አኑሬያችኋለው፤ ከአሁን በኃላ ግን ምትኖሩበት ቦታ ፈልጉ ›› ትለናለች ብለው ነበር የጠበቁት፡፡ይሄንን ጉዳይ እሷ ቤት በማትኖርበት ጊዜ እያነሱ ተወያይተውበታል..ለዛ ነው በፍጥነት ወደሁለቱም ምናብ ሀሳቡ የመጣው፡፡
‹‹ልጆች በጣም እንደምወዳችሁ ታውቃላችሁ አይደል?››
‹‹አዎ እናውቃለን፡፡ እኛም በጣም እንወድሻለን››ሲል የመለሰላት ናኦል ነበር፤ኑሀሚ ግን ይሄንን ቤት ለቀው ከወጡ በኃላ ምን ማድረግ እንዳለበባቸው ስታሰላስል ነበር፡፡ደግማኛ ወንድሟን ይዛ ወደበረናዳ ለመመለስ ፈፅሞ ፍቃደኛ አልነበረችም፡፡ትንሽም ቢሆን የራሳቸው ቤት ተከራተው መኖር እንዳለባቸው ከወሰነች ሰነባብታ ነበር፡፡ለዛ ኪራይ ቤት ክፍያ ሚሆን ገንዘብ ለማግኘት ደግሞ ማንኛውንም ስራ ለመስራት ፍቃደኛ ነበረች፡፡ ለወንድሟ ስትል ብትሰርቅም ብትገድልም ግድ አልነበራትም፡፡
ምስራቅ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ይሄውላችሁ ምን መሳላችሁ…አንደእኔ እንደእኔ ዘላለም እዚሁ አንድ ላይ እንዲህ እየተሳሰብን በፍቅርና በደስታ መኖር ብንችል ደስ ይለኝ ነበር… ግን ያው ታውቃላችሁ አይደል?››
ቀጥታ ወደጉዳዩ ገባች‹‹ማለት የምትፈልገውን ፍርታ ማለት ባለመቻሏ ሁለቱም ላይ ጭንቀት ፈጠረች…ኑሀሚ ፈጠን አለችና‹‹ይገባናል..እስከዛሬ ስለተንከባከብሽንና በዚህ ሁኔታ እንድናገግምና ስለወደፊታችን እንድናስብ ስላደረግሽን የላለም ባለውለታችን ነሽ፤ግን ወንድሜን ይዤ ወደበረንዳ መውጣት አልፈልግም…ከቻልሽ ለእኛ ምትሆን ትንሽ ቤት
ተከራይተን መኖር እንድንችል አግዢን፡፡ማንኛውንም ያገኘነው ስራ በመስራት የቤት ኪራዩን በመክፈል እራሳችንን ማኖር አያቅተንም…እቤት ካገኘን ነገ ተነገ ወዲያ እንሄዳለን..አንቺ አታስቢ››
ምስራቅ ፈገግ አለች‹‹እንዳዛ ማለቴ አይደለም፡፡እኔ እንደምታዩት እዚህ የምኖረው ብቻዬን ነው፡፡ ቤቱም ሰፊና ለሁላችንም የሚበቃ ነው፡፡እዚህ ከእኔ ጋር በመኖራችሁ በጣም ተጠቃሚው እናናተ ሳትሆኑ እኔ ነኝ….ግን ለእናንተ የወደፊት ህይወት ሲባል የተለየ መንገድ መከተል አለብን፡፡››
ሁለቱም ስሜታቸው ይበልጥ ተናቃቃ፡፡የምትላቸው በፍፅም እየገባቸው አይደለም፡፡
‹‹አልገባንም›› አለች..ኑሀሚ፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ምስራቅ ኮስተር ብላ ‹‹አትልፈስፈስ…ጠንከር ብለህ መሆን ስለሚገባው ነገር ብቻ እንነጋር፡፡››አለችው፡፡
ናኦልም‹‹ምን የሚሆን ነገር አለና እንነጋራለን…በዚህ ምድር ላይ አንድ አለቺኝ የምላት እህቴን እንዲህ ባለ ሁኔታ አጥቼያት እኔስ በህይወት መኖሬን ቀጥላለው?››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹አይዞህ ኑሀሚ እንደዚህ ካሉ ብዙ አደጋዎች ሰርቫይቭ የማድረግ ልምድ ያላት ልጅ ነች፤ደግሞ በምድር ላይ ያለችህ እሷ ብቻ አይደለችም..እኔም እኮ ስላለሁ መሰለኝ አሁን በዚህ የሀዘንህ ወቅት አጠገብህ ያለሁት፡፡
‹‹እሱማ እውነትሽን ነው፡፡››
‹‹እኮ ..በል ተነስና መልስ እንመልስለት፡፡››
ከተዘረፈጠበት ተነሳና ወደእሷ ቀረበ‹‹ምን ብለን?››
‹‹ያልከኸውን አደርጋለው..ለማንም ሳልናገር ያልከው ሀገር ድረስ እመጣለሁ..ግን እህቴ በህይወት መኖሯን በምን አውቃለሁ?አንድ ማረጋገጫ ስጠኝ፡፡››
‹‹አዎ እንደዛ ብንለው ይሻላል አይደል…?ወይ ተጨማሪ ፎቶ ወይ ቪዲዬ ይልክልናል፡፡ወይ ደግሞ በስልክም ሊያገናኘን ይችላል፡፡››
‹‹በቃ ራስሽ ፃፊው››
እንደማሰብ አለችና ፃፈችና ላከች፡፡መልስ እስኪመጣ ለመጠበቅ ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ፡፡ለሁለቱም የሚጠጣ ቢራ አቀረበና እሱን እየጠጡ በትካዜ በስልኩ ከአሁን አሁን የሚላከውን ኢሜል መጠበቅ ቀጠለ፡፡
ከሶስት ሰዓት በኃላ ተጨማሪ ፎቶ ተላከላቸው፡፡እንሱ ያላወቁት እነዛ ፎቶዎች የተመረጡት ከኑሀሚ ስልክ ውስጥ በፔሩ ቆይታዋ በተያዩ ጊዜያቶች ከተነሳቸው ውስጥ የተመረጡትን ነው፡፡
ከፎቶ ጋር አጭር መልዕክት ተልዕኮል
‹‹ባቀረብንልህ ሀሳብ ከተስማማን አሁኑኑ አሳውቀን፡፡››ይላል፡፡
‹‹እ ምን አሰብሽ? ››አለት፡፡ ከምስራቅ የተሻለ ሀሳብ ለማግኘት እየተመኘ ጠየቃት.. ምርጫ የለንም ‹‹ተስማምቼያለሁ ብለህ ላክላቸው፡፡››እንዳለችው አደረገ፡፡
በል የጉዞ ሰነዶችህን አዘጋጅ…በሶስት ቀን ውስጥ አስፈላጊውን ገንዘብ ስለምንልክልህ ሙሉ ስምህን እና አስፈላጊ መረጃዎችን ላክልን፡፡እንደተነጋገርነው ግን ይሄንን ሚስጥር ሌላ ለሶስተኛ ወገን ለመንግስት አሳልፈህ ብትሰጥ ነገሮች ሁሉ ያከትምላቸዋል….ከዛ በኃላ
እህትህን በዚህ ምድር ላይ ዳግመኛ የማግኘት እድልህ ከዜሮ በታች ይሆናል…በል ፍጠን ይላል፡፡
‹‹አነበብሽው አይደል?››
‹‹አዎ ..አነበብኩት..››አለችና ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡
‹‹ምነው? ››
‹‹ልሄድ ነው፡፡››
‹‹ልሄድ ነው በእንደዚህ አይነት በተሰባበርኩበት ሁኔታ ላይ ሆኜ ጥለሺኝ ልትሄጂ ነው….፡፡››
‹‹ጎረምሳው ተረጋጋ እንጂ ..ይልቅ እራስህን ለረጅምና አስቸጋሪ ጉዞ አዘጋጅ፡፡እኔ ሄጄ ለጉዞ አስፈላጊ የሆኑ ፖስፖርትና ቢዛዎችን ላዘጋጅ፡፡ ታውቃለህ እነዚህን የጉዞ ሰነዶች በአሁኑ ጊዜ በስድስት ወር ውስጥም ማግኘት አይቻልም፡፡አኔ ደግሞ ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማግኘት
አለብኝ፡፡ ለዚህ ደግሞ ደቂቃዎችን ሳላባክን ከአሁን ያለኝን ኃይልና መስመር ሁሉ ተጠቅሜ ማሳካት መቻል አለብኝ…እ ምን ትላለህ ጎረምሳው?››
ተንደረደረ ሄደና ተጠመጠመባት፡፡እሷም እጆቾን በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመቻቸው… ጭምቅ አደረጋት፡፡
‹‹አንቺ ስላለሺኝ ሁሌ ደስተኛ ነኝ፡፡ዘላለም በእቅፍሽ ውስጥ መኖር ነው ምኞቴ…በጣም ነው የምወድሽ….››አላት
‹‹….ተራጋጋ፡፡ከዚህ በላይ ከወራን እንባዬ ያመልጠኛል፡፡››አለችና ከእቅፉ ወጥታ ፈዞ በቆመበት ፊቷን አዙራ ወጥታ ሄደች፡፡በቦዘዙ አይኖቹ በስስት እያያት በሀሳቡ ሸኛት፡፡..
///
ከሶስት ቀን በኃላ በአለምአቀፍ የሀዋላ አስተላላፊዎች አማካይነት 50 ሺ ዶላር ተላከለት፡፡ያልጠበቀው ነገር ነበር፡፡ብሩ ሲደርሰው ነገሩ ሲሪዬስ እንደሆነ እሱ ብቻ ሳይሆን ምስራቅም ተገነዘበች፡፡ሁለቱም መመለስ ያቃቸው ይሄ ሁሉ አጋቾቹ ይሄን ሁሉ ኢንቨስትመንትና ጥረት የሚያደርጉት ከእሷ ምን ፈልገው ነው? የሚለውን ነው ፤የእሱንስ ወደፔሩ መሄድ ለምን ፈለጉት?››በተለይ ይሄን ጥያቄ ከአንደበቷ አውጥታ ለእሱ አትንገረው እንጂ ምስራቅንም በጣም ነው ያሳሰባት፡፡
ናኦል ገንዘቡ እንደደረሰው ካወቀ በኃላ እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም፡፡ሰዓቱ ገፍቶ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኖኛል በተኛበት አልጋ ላይ እየተገላበጠ በትዝታ ወደኃላ ወደልጅነታቸው ተጓዘ፡፡ምስራቅ እሱና ተወዳጅ እህቱን ከጎዳና አንስታ እንዴት ሰላይ እዳደረገቻቸው በዝርዝር ትዝ አለው፡፡
ከ15 አመት በፊት ምስራቅ የወንድሜ ቤት ነው ብላ ከጓዳና አንስታ ጎተራ የሚገኝ ኮንደምንዬም ቤት ከወሰደቻቸው በኃላ ከአዛው ቤት ሳይወጡ ሁለት ወር ሙሉ ቆይተው
ነበር፡፡ በሶስተኛው ወር ግን ማታ እራት በልተው ቴሌቬዥን እያዩ እያለ ድንገት ሪሞቱን አንስታ ቴሌቪዝኑን አጠፋችና ፊት ለፊታቸው ቁጭ አለች፡፡
እህትና ወንድም እርስበር ተያዩ ፡፡የሆነ ነገር ልትነግራቸው እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡፡ግን የጠረጠሩት በቃ እስካሬ ለሁለት ወር በምቾትና በድሎት በወንድሜ ቤት አኑሬያችኋለው፤ ከአሁን በኃላ ግን ምትኖሩበት ቦታ ፈልጉ ›› ትለናለች ብለው ነበር የጠበቁት፡፡ይሄንን ጉዳይ እሷ ቤት በማትኖርበት ጊዜ እያነሱ ተወያይተውበታል..ለዛ ነው በፍጥነት ወደሁለቱም ምናብ ሀሳቡ የመጣው፡፡
‹‹ልጆች በጣም እንደምወዳችሁ ታውቃላችሁ አይደል?››
‹‹አዎ እናውቃለን፡፡ እኛም በጣም እንወድሻለን››ሲል የመለሰላት ናኦል ነበር፤ኑሀሚ ግን ይሄንን ቤት ለቀው ከወጡ በኃላ ምን ማድረግ እንዳለበባቸው ስታሰላስል ነበር፡፡ደግማኛ ወንድሟን ይዛ ወደበረናዳ ለመመለስ ፈፅሞ ፍቃደኛ አልነበረችም፡፡ትንሽም ቢሆን የራሳቸው ቤት ተከራተው መኖር እንዳለባቸው ከወሰነች ሰነባብታ ነበር፡፡ለዛ ኪራይ ቤት ክፍያ ሚሆን ገንዘብ ለማግኘት ደግሞ ማንኛውንም ስራ ለመስራት ፍቃደኛ ነበረች፡፡ ለወንድሟ ስትል ብትሰርቅም ብትገድልም ግድ አልነበራትም፡፡
ምስራቅ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ይሄውላችሁ ምን መሳላችሁ…አንደእኔ እንደእኔ ዘላለም እዚሁ አንድ ላይ እንዲህ እየተሳሰብን በፍቅርና በደስታ መኖር ብንችል ደስ ይለኝ ነበር… ግን ያው ታውቃላችሁ አይደል?››
ቀጥታ ወደጉዳዩ ገባች‹‹ማለት የምትፈልገውን ፍርታ ማለት ባለመቻሏ ሁለቱም ላይ ጭንቀት ፈጠረች…ኑሀሚ ፈጠን አለችና‹‹ይገባናል..እስከዛሬ ስለተንከባከብሽንና በዚህ ሁኔታ እንድናገግምና ስለወደፊታችን እንድናስብ ስላደረግሽን የላለም ባለውለታችን ነሽ፤ግን ወንድሜን ይዤ ወደበረንዳ መውጣት አልፈልግም…ከቻልሽ ለእኛ ምትሆን ትንሽ ቤት
ተከራይተን መኖር እንድንችል አግዢን፡፡ማንኛውንም ያገኘነው ስራ በመስራት የቤት ኪራዩን በመክፈል እራሳችንን ማኖር አያቅተንም…እቤት ካገኘን ነገ ተነገ ወዲያ እንሄዳለን..አንቺ አታስቢ››
ምስራቅ ፈገግ አለች‹‹እንዳዛ ማለቴ አይደለም፡፡እኔ እንደምታዩት እዚህ የምኖረው ብቻዬን ነው፡፡ ቤቱም ሰፊና ለሁላችንም የሚበቃ ነው፡፡እዚህ ከእኔ ጋር በመኖራችሁ በጣም ተጠቃሚው እናናተ ሳትሆኑ እኔ ነኝ….ግን ለእናንተ የወደፊት ህይወት ሲባል የተለየ መንገድ መከተል አለብን፡፡››
ሁለቱም ስሜታቸው ይበልጥ ተናቃቃ፡፡የምትላቸው በፍፅም እየገባቸው አይደለም፡፡
‹‹አልገባንም›› አለች..ኑሀሚ፡፡
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ይዘውት የሄዱት ቦታ ከቢሾፍቱ ከተማ በባቦጋያ ሀይቅ አካባቢ ከከተማው ወጣ ብሎ የሚገኝ ቪላ ነው፡፡ይህ ቪላ ቤተሰቡ ከውጥረት ረገብ ለማለት ሲፈልግ የሚገለገልበት ስፋራ ነው፡፡ለአለፉት አንድ አመት ከግማሽ ማንም ዝር ብሎበት አያውቅም ነበር፡፡ሰለሞን ስፍራውን ሲያይ ከውበትም ሆነ ከፀጥታ አንፃር ሲታይ ሙሉ በሙሉ እሱ እንደሚፈልገው አይነት ሆኖ ነው ያገኘው፡፡አንድ ሺ ካሬ ሜትር በላይ የሚሆን ቅፅር ግቢ ነው፡፡መሀከል ላይ ግዙፍና ባለግርማ ሞገስ ጥንታዊ ግን ደግሞ ጥሩ ይዞታ ላይ ያለ ግዙፍ ቪላ ቤት አለበት…ግቢው ውስጥ እድሜ ጠገብ ግዙፍ ባለግርማ ሞገስ የባህር ዛፍና የጥድ ዛፎች ስብስባ ላይ እንደተቀመጠ ታዳሚ እዚህም አዛም ዙሪያውን ተሰራጭተው ይታያሉ…ገና ግቢውስጥ ገብተው እንዳቆሙ የቤት ጠባቂዎች በልና ሚስቶች በፍጥነት መጥታው መኪናዋ አጠገቡ ቆሙ፡፡መኪናዋን ሲነዳ የነበረው እራሱ ሰሎሞን ስለነበረ….ሞተሩን
አጠፋና ቀድሞ ወረደ…አቶ ኃይለመለኮትን ወ.ሮ ስንዱም ወረዱና ከጠባቂዎቹ ጋር ሰላምታ መለዋወጥ ጀመሩ…ከዛ ቀጥታ ወደ ቤት ነው የገቡት….ቀድመው ደውለው ስለነበር..እቤቱ ምሉ በሙሉ ፀድቶና የእነሱም መኝታ ክፍል ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው….
ታፈሰ ‹‹ጋሼ ባዘዙኝ መሰረት ሶስት ክፍል ለመኝታ አዘጋጅቼያለው…ይሄው እርሶ እዚህ ግቡ….እትዬ ደግሞ ቀጥሎ ያለው …ወንድም አንተ ደግሞ የፊት ለፊተኛው ክፍል…..ድንገት ስለሆነብን ሁሉንም ነገር ማዘጋጀት አልቻልንም….የጎደለውን ንገሩኝና ከተማ ወጣ ብዬ ገዝቼ አሟላላሁ››
አቶ ሃይለመለኮት ወደሰለሞን እያመለከቱ‹‹ተፈሰ…ይሄውልህ እዚህ 15 ቀን ነው የምንቆየው….በዚህ 15 ቀናት ውስጥ የእኛም ሆነ የአንተ ሀለቃ እሱ ነው….ምንም ነገር ቢያዝህ እሱ ያለውን ነው የምታደርገው…እኛም እንደዛው››ሲሉ መመሪያ አስተላለፉ፡፡
ታፈሰ…የአቶ ኃይለልዕልን ንግግር ከበፊት ቆፍጣና ባህሪያቸው ጋር አልሄድ ስላለው ..ግራ በመጋባት አፍጥጦ ያያቸው ጀመር…እሱ እንደሚየውቀው እኚ ግዙፍ አዛውንት ለሰው ምንም ሊሰጡ ይችላሉ የአዛዥነት ቦታቸውን ግን ፈፅሞ ሸርፈው እንኳን ለሌላ ሰው ይሰጣሉ ብሎ ማመን ይከብደዋል፡፡
‹‹ታፈሰ ..ሰምተኸኛል…የሁሉ ነገር አዛዣችን እሱ ነው››ደገሙለት፡፡
‹‹አዎ ..ገባኝ ጌታዬ…እንዳሉት ይደረጋል››
‹‹አሁን ሁላችንም ወደክፍላችን እንግባና ትንሽ አረፍ እንበል ..አይደል?››ወ.ሮ ስንዱ የሰለሞንን አይኖች በልምምጥ እያዩ ጠየቁ፡፡
ቆይ አንዴ ክፍላችሁን ልይ ብሎ..ለአቶ ኃይለልኡል የተመደበውን ከፍቶ አየው፡፡ቀጥሎ የወ.ሮ ስዱን ከፈተና አየው፡፡‹‹ጥሩ በቃ ግቡና እረፉ››
ሁለቱም ገቡና የየራሳቸውን ክፍል ዘጉ
‹‹አንተም ወደክፍልህ ግባ ጌታዬ..እኔ ደግሞ እቃችሁን ከመኪና ላውርድ››
‹‹ቆይ አብሬህ ልምጣ››ብሎ ተከተለው፡፡የታፈሰ ባለቤት ለእንግዶቹ ምግብ እያበሰለች ስለነበር ታፈሰ እቃዎቹን ማለት ይዘው የመጡትን አስቤዛ እና ሻንጣዎች ሲያወርድና ወደቤት ሲያስገባ ሰሎሞን አገዘው፡፡እንደጨረሱ፡፡‹‹ተለቅ ያለ ክፍል የለም?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ምን አይነት ክፍል…ማለቴ ለምን የሚሆን?››
‹‹ለመኝታ ቤት የሚሆን ..ሁለት አልጋ የሚያዘረጋ››
‹‹ቆይ ..ኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ያለው ክፍል ሰፋ ይላል››
‹‹ማየት እችላለሁ?››
‹‹አዎ ይቻላል….››ብሎ ይዞት ሄደና ከፈተለት…ሰለሞን ወደውስጥ ዘልቆ ሳይገባ በራፉ ላይ በመቆም አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ተመለከተው….አቦራ የጠጣና ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቢሆንም የሚፈልገው አይነት ክፍል ነው፡፡››
‹‹ታፈሰ ይሄንን ክፍል በአስቸኳይ ልታስፀዳልኝ ትችላለህ….?››
‹‹እችላለሁ..አፀዳዋለው››
‹‹አይ ብቻህን ይከብድሀል..ሰው ቅጠርና በፍጥነት ወለሉም ግድግዳውም ይፅዳ….ውስጥ ያሉት እቃዎችም ወደሌላ ክፍል ይዘዋወሩ››
‹‹እሺ››
ተሰናብቶት ንፁህ አየር ሊቀበልና እግረመመንገዱን አካባቢውን ለመቃኘት ወጥቶ ሄደ፡፡
///
በማግስቱ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ሁለቱንም የማይጣጣሙ ባለትዳሮችን አንድ ክፍል ጎን ለጎን እንዲቀመጡ አደረገና እሱ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ..ጉሮሮውን አፀዳዳና የመግቢያ ንግግሩን ጀመረ
‹‹በሰዎች መካከል ለተለያየ አለማ ተብለው የሚደረጉ የእርስ በርስ ጉድኝቶችና ቁርኝቶች አሉ፡፡ከነዛ መካከል ግን በጣም ውስብስቡ የጠበቀውና የጠለቀው ግንኙነት በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጠር የጋብቻ ጉድኝት ነው፡፡በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ሁሉ ጊዜ ቀላል የተባለ መንገድ አይገኝም….አንዱ ጋብቻ ውስጥ የሚፈጠረው ችግር ከሌላው ጋብቻ ችግር በአይነትም በይዘትም ፍፁም የተለየ በመሆን ችግሩን ለማስተካከል የሚወሰደውም እርምጃ የዛኑ ያህል የተለያ ነው፡፡በዛ ላይ ሁሉም ችግሮች እዲፈቱ በጥንዶቹ መካከል ስክነት፣ ትዕግስትን፣ጥረትን እና እራስ መግዛትን
ይጠይቃል፡፡አሁን ልብ በሉ ፣ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደልም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቃችሁ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር የለብንም፡፡
እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራች ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ገና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም ..አዎ አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ሌላው በምንም አይነት ሁኔታ ንግግራችሁ ሰው ፊት አይሁን፡፡የምንወደው ሰው ላይ ያለንን ቅሬታ ብቻውን በሆነበት ጊዜ ነው መናገር ያለብን…እንደዛ ሲሆን ነው ውጤታማና ጥፈቱን ለማረም ፍቃደኛ የሚሆነው…ወቀሳው..ሰው ፊት ሲሆን ግን ሰውዬው የበለጠ በእኛ ቅሬታ እንዲያድርበት መንገድ ያመቻቻል፡፡
‹‹እንግዲ ሁላተችሁም እንደምታውቁት አሁን ለእኛ እዚህ መገኘት ዋናዋ ምክንያት በፀሎት ነች፡፡እኔ በስራ በተለይ ከሀገር ውጭ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ብዙ ባለትዳሮችን አማክሬያለሁ ትዳራችውም መካከል ያለውን ችግር በመተጋገዝ ለመፍታት ችያለሁ....በብዙዎችም ረክቼለው..ከብዙ ቤተሰቦች ጋርም እቤተሰብ ለመሆን ችያለው….ግን እመኑኝ እንዲህ እንደእናነተ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኝ አያውቅም››
‹‹የተለየ ስትል?››
(አቃቂ እና ቦሌ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ይዘውት የሄዱት ቦታ ከቢሾፍቱ ከተማ በባቦጋያ ሀይቅ አካባቢ ከከተማው ወጣ ብሎ የሚገኝ ቪላ ነው፡፡ይህ ቪላ ቤተሰቡ ከውጥረት ረገብ ለማለት ሲፈልግ የሚገለገልበት ስፋራ ነው፡፡ለአለፉት አንድ አመት ከግማሽ ማንም ዝር ብሎበት አያውቅም ነበር፡፡ሰለሞን ስፍራውን ሲያይ ከውበትም ሆነ ከፀጥታ አንፃር ሲታይ ሙሉ በሙሉ እሱ እንደሚፈልገው አይነት ሆኖ ነው ያገኘው፡፡አንድ ሺ ካሬ ሜትር በላይ የሚሆን ቅፅር ግቢ ነው፡፡መሀከል ላይ ግዙፍና ባለግርማ ሞገስ ጥንታዊ ግን ደግሞ ጥሩ ይዞታ ላይ ያለ ግዙፍ ቪላ ቤት አለበት…ግቢው ውስጥ እድሜ ጠገብ ግዙፍ ባለግርማ ሞገስ የባህር ዛፍና የጥድ ዛፎች ስብስባ ላይ እንደተቀመጠ ታዳሚ እዚህም አዛም ዙሪያውን ተሰራጭተው ይታያሉ…ገና ግቢውስጥ ገብተው እንዳቆሙ የቤት ጠባቂዎች በልና ሚስቶች በፍጥነት መጥታው መኪናዋ አጠገቡ ቆሙ፡፡መኪናዋን ሲነዳ የነበረው እራሱ ሰሎሞን ስለነበረ….ሞተሩን
አጠፋና ቀድሞ ወረደ…አቶ ኃይለመለኮትን ወ.ሮ ስንዱም ወረዱና ከጠባቂዎቹ ጋር ሰላምታ መለዋወጥ ጀመሩ…ከዛ ቀጥታ ወደ ቤት ነው የገቡት….ቀድመው ደውለው ስለነበር..እቤቱ ምሉ በሙሉ ፀድቶና የእነሱም መኝታ ክፍል ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው….
ታፈሰ ‹‹ጋሼ ባዘዙኝ መሰረት ሶስት ክፍል ለመኝታ አዘጋጅቼያለው…ይሄው እርሶ እዚህ ግቡ….እትዬ ደግሞ ቀጥሎ ያለው …ወንድም አንተ ደግሞ የፊት ለፊተኛው ክፍል…..ድንገት ስለሆነብን ሁሉንም ነገር ማዘጋጀት አልቻልንም….የጎደለውን ንገሩኝና ከተማ ወጣ ብዬ ገዝቼ አሟላላሁ››
አቶ ሃይለመለኮት ወደሰለሞን እያመለከቱ‹‹ተፈሰ…ይሄውልህ እዚህ 15 ቀን ነው የምንቆየው….በዚህ 15 ቀናት ውስጥ የእኛም ሆነ የአንተ ሀለቃ እሱ ነው….ምንም ነገር ቢያዝህ እሱ ያለውን ነው የምታደርገው…እኛም እንደዛው››ሲሉ መመሪያ አስተላለፉ፡፡
ታፈሰ…የአቶ ኃይለልዕልን ንግግር ከበፊት ቆፍጣና ባህሪያቸው ጋር አልሄድ ስላለው ..ግራ በመጋባት አፍጥጦ ያያቸው ጀመር…እሱ እንደሚየውቀው እኚ ግዙፍ አዛውንት ለሰው ምንም ሊሰጡ ይችላሉ የአዛዥነት ቦታቸውን ግን ፈፅሞ ሸርፈው እንኳን ለሌላ ሰው ይሰጣሉ ብሎ ማመን ይከብደዋል፡፡
‹‹ታፈሰ ..ሰምተኸኛል…የሁሉ ነገር አዛዣችን እሱ ነው››ደገሙለት፡፡
‹‹አዎ ..ገባኝ ጌታዬ…እንዳሉት ይደረጋል››
‹‹አሁን ሁላችንም ወደክፍላችን እንግባና ትንሽ አረፍ እንበል ..አይደል?››ወ.ሮ ስንዱ የሰለሞንን አይኖች በልምምጥ እያዩ ጠየቁ፡፡
ቆይ አንዴ ክፍላችሁን ልይ ብሎ..ለአቶ ኃይለልኡል የተመደበውን ከፍቶ አየው፡፡ቀጥሎ የወ.ሮ ስዱን ከፈተና አየው፡፡‹‹ጥሩ በቃ ግቡና እረፉ››
ሁለቱም ገቡና የየራሳቸውን ክፍል ዘጉ
‹‹አንተም ወደክፍልህ ግባ ጌታዬ..እኔ ደግሞ እቃችሁን ከመኪና ላውርድ››
‹‹ቆይ አብሬህ ልምጣ››ብሎ ተከተለው፡፡የታፈሰ ባለቤት ለእንግዶቹ ምግብ እያበሰለች ስለነበር ታፈሰ እቃዎቹን ማለት ይዘው የመጡትን አስቤዛ እና ሻንጣዎች ሲያወርድና ወደቤት ሲያስገባ ሰሎሞን አገዘው፡፡እንደጨረሱ፡፡‹‹ተለቅ ያለ ክፍል የለም?››ሲል ጠየቀው፡፡
‹‹ምን አይነት ክፍል…ማለቴ ለምን የሚሆን?››
‹‹ለመኝታ ቤት የሚሆን ..ሁለት አልጋ የሚያዘረጋ››
‹‹ቆይ ..ኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ያለው ክፍል ሰፋ ይላል››
‹‹ማየት እችላለሁ?››
‹‹አዎ ይቻላል….››ብሎ ይዞት ሄደና ከፈተለት…ሰለሞን ወደውስጥ ዘልቆ ሳይገባ በራፉ ላይ በመቆም አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ተመለከተው….አቦራ የጠጣና ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቢሆንም የሚፈልገው አይነት ክፍል ነው፡፡››
‹‹ታፈሰ ይሄንን ክፍል በአስቸኳይ ልታስፀዳልኝ ትችላለህ….?››
‹‹እችላለሁ..አፀዳዋለው››
‹‹አይ ብቻህን ይከብድሀል..ሰው ቅጠርና በፍጥነት ወለሉም ግድግዳውም ይፅዳ….ውስጥ ያሉት እቃዎችም ወደሌላ ክፍል ይዘዋወሩ››
‹‹እሺ››
ተሰናብቶት ንፁህ አየር ሊቀበልና እግረመመንገዱን አካባቢውን ለመቃኘት ወጥቶ ሄደ፡፡
///
በማግስቱ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ሁለቱንም የማይጣጣሙ ባለትዳሮችን አንድ ክፍል ጎን ለጎን እንዲቀመጡ አደረገና እሱ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ..ጉሮሮውን አፀዳዳና የመግቢያ ንግግሩን ጀመረ
‹‹በሰዎች መካከል ለተለያየ አለማ ተብለው የሚደረጉ የእርስ በርስ ጉድኝቶችና ቁርኝቶች አሉ፡፡ከነዛ መካከል ግን በጣም ውስብስቡ የጠበቀውና የጠለቀው ግንኙነት በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጠር የጋብቻ ጉድኝት ነው፡፡በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ሁሉ ጊዜ ቀላል የተባለ መንገድ አይገኝም….አንዱ ጋብቻ ውስጥ የሚፈጠረው ችግር ከሌላው ጋብቻ ችግር በአይነትም በይዘትም ፍፁም የተለየ በመሆን ችግሩን ለማስተካከል የሚወሰደውም እርምጃ የዛኑ ያህል የተለያ ነው፡፡በዛ ላይ ሁሉም ችግሮች እዲፈቱ በጥንዶቹ መካከል ስክነት፣ ትዕግስትን፣ጥረትን እና እራስ መግዛትን
ይጠይቃል፡፡አሁን ልብ በሉ ፣ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደልም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቃችሁ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር የለብንም፡፡
እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራች ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ገና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም ..አዎ አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ሌላው በምንም አይነት ሁኔታ ንግግራችሁ ሰው ፊት አይሁን፡፡የምንወደው ሰው ላይ ያለንን ቅሬታ ብቻውን በሆነበት ጊዜ ነው መናገር ያለብን…እንደዛ ሲሆን ነው ውጤታማና ጥፈቱን ለማረም ፍቃደኛ የሚሆነው…ወቀሳው..ሰው ፊት ሲሆን ግን ሰውዬው የበለጠ በእኛ ቅሬታ እንዲያድርበት መንገድ ያመቻቻል፡፡
‹‹እንግዲ ሁላተችሁም እንደምታውቁት አሁን ለእኛ እዚህ መገኘት ዋናዋ ምክንያት በፀሎት ነች፡፡እኔ በስራ በተለይ ከሀገር ውጭ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ብዙ ባለትዳሮችን አማክሬያለሁ ትዳራችውም መካከል ያለውን ችግር በመተጋገዝ ለመፍታት ችያለሁ....በብዙዎችም ረክቼለው..ከብዙ ቤተሰቦች ጋርም እቤተሰብ ለመሆን ችያለው….ግን እመኑኝ እንዲህ እንደእናነተ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኝ አያውቅም››
‹‹የተለየ ስትል?››
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
================
ሰሎሜና ሂሩት እንደተባባሉት ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ .. ሂሩት በሰበቡ እነሱ ቤት እንደምታድር ለአላዛር ነግራው በሰዓቱ እንድትገኝ አደረገች፡፡እራት በልተው መጠጥ እየቀማመሱ ካመሹ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ከእናትዬው እንደተደወለላትና እንዳመማቸው በመናገር ብቻቸውን ትታቸው ሄደች፡፡ አላዛር ልከተልሽ ቢላትም እምቢ አለችው፡፡ቀጥታ እናቷ ቤት ሳይሆን ቀን ወደዘጋጀችው ከሰፈራቸው ብዙም የማይርቅ ሆቴል ነበር የሄደችው፡፡ቀጥታ የተከራየችው ቤርጎ ገብታ ምን ይፈጠር ይሆን እያለች ስትጨነቅና ስትገላበጥ አደረች፡፡እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር ነበር ንጊቱን የሚያበስሩ የወፎችን ዝማሬ የሰማችው…ሂሩትም ገና ሰማይና ምድሩ በቅጡ ሳይላቀቅ ከለሊቱ 12 ሰዓት አካበቢ ነበር የደወለችላት፡፡ወዲያው ክፍሏን ለቃ ወጣችና የሆቴሉ ፓርኪንግ ጋር ያቆመቻትን መኪና ውስጥ ገብታ ወደነገረቻት ቦታ ተፈተለከች፡፡በወቅቱ የተከፈተ ካፍቴሪያ ወይም ሆቴል ማግኘት ስላልቻሉ ሰሎሜ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው ነበር ያወሩት፡፡
ሶሎሜ ስታገኛት ፈክታና ተፍለቅልቃ አገኛታለሁ ብላ ነበር ያሰበችው..ግን አኩርፋና ለምቦጯን ጥላ ነው ያገኘቻት፡፡ይሄ ደግሞ ይበልጥ አስደነገጣት፡፡‹‹የሆነ ነገር ባይፈጠርማ እንደዚህ አትነፋፋም ነበር፡፡በቃ ተሳክቶላት አሳስተዋለች..በቃ ችግሩ ከእኔ ነው››ብላ ደመደመች፡፡ድምጽ አውጥታ ብትጮህ ወይም እንባዋን ዘርግፋ ብታለቅስ ደስ ይላት ነበር፡፡ግን እንደዛ በማድረግ ሂሩት ፊት ደካማ ሆና መታየት አልፈለገችም፡፡
ከአሁን አሁን አንደበቷን አላቃ የሆነ ነገር ትለኛለች ብላ ብትጠብቅ ዝም ብላ እንዳቀረቀረች የቀኝና የግራ እጇን መዳፎች አንድ ላይ አቆላልፋ እያፍተለተለች ነው፡፡እሷን እንድትናገር መጠበቁ አሰልቺ ሆኖ ስለታያት‹‹እሺ እንዴት ሆነ?››በማለት ቃል አወጣችና ጠየቀቻት፡፡
‹‹በፊትም ተይ ይቅርብኝ ያልኩሽ ይሄን ፈርቼ ነበር…››እንባዋን ዘረገፈችው፡፡
‹‹አይዞሽ ..ምንም የሚያስለቅስ ነገር እኮ የለም..ምንም ነገር ሊፀፅትሽ አይገባም…እኔ እራሴ ፈቅጄና ገፋፍቼ እኮ ነው እንድታደርጊ ያደረኩሽ…አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆኖልኛል…… ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ›› አለቻት፡፡
ከአንደበቷ እየተወረወረ የሚወጣው ቃል ለራሷ እራሱ ሻካራነቱ እየተሰማት ነበር..እስከዛሬ ለሌላ ሰው ከተናገረቻቸው ንግግሮች እጅግ መራሩ ንግግር ነው፡፡እንደውም ንግግር እንዲህ ሊመር እንደሚችል ሲሰማት የመጀመሪያ ቀን የህይወት ልምዷ ነበር፡፡
ሂሩት የሆነ ነገር ትላለች ብላ ስትጠብቅ እሷ ግን እጇን ወደኪሷ ከተተችና ሞባይሏን በማውጣት ከፈተችና ሰጠቻት፡፡
‹‹ምንድነው?››
‹‹እይው በቃል ከምነግርሽ በምስል ይሻላል ብዬ አንቺ ከወጣሽ በኃላ ያለውን ትእይንት ሁሉ እሱ ሳያውቅ ቀርጬዋለሁ››
‹‹ምን ሊያደርግልኝ ነው የማየው?‹‹ገና ስታስበው ዘገነናት…የገዛ ባሏ… ቀለበት እጣቷ ላይ አጥልቆ ያጫት፤ ቬሎ ሰውነቷ ላይ አልብሶ ያገባትና አንድ ቀን ጭኗን ፈልቅቆ ማያውቀው ሰው አሁን ፊት ለፊቷ የተቀመጠችውን የገዛ ጓደኛዋን እርቃን ሰውነቷን አቅፎ ፤ቅስር ጡቶቻን እየጠባ…መቀመጫዋን እየጨመቀ…ሲያስጮኸት…እላዮ ላይ ወጥቶ ..ሁለቱም በስሜት እሳት ግለው ነበልባሉ በዙሪያቸው ሲንበለበል በምናቧ ሳላችና ዝግንን አላት..እንደምንም የሰጠቻትን ሞባይል አስጠግታ የተቀረፀውን ማየት ጀመረች፡፡ከጠበቀችው ፈፅሞ ተቃራኒ የሆነ ነገር ነው እያየች ያለችው፡፡
ሂሩት እየደነሳች ተራ በታራ ልብሷን ስታወልቅ…አላዛር ፊቱን ስልኩ ላይ አቀርቅሮ እሷን ላለማየት ሲጠነቀቅና ሲሸማቀቅ…እርቃኗን ሔዳ ስልኩን ከእጁ ነጥቃ ወደሶፋው ወርውራ እላዩ ላይ ለመቀመጥ ስትሞክር፤ከላዩ ላይ ወርውሮ ወለል ላይ ጥሏት እየተንዘረዘረ ሲናገር‹‹አንቺ ምን አይነት ክፉ ሴት ነሽ..ጓደኛሽ አንቺን አምና እኮ ነው ባሏን ጥላልሽ የሄደችው…እኔ እንኳን ልሳሳት ፈቅጄ ባስቸግርሽ አንቺ ትሞክሪዋለሽ ብዬ አስቤ አላውቅም..ደግሞ ከነዛ ሀሉ ጓደኞቾ አንቺን መርጣ ሚዜ ማድረጓ..?አዝናለሁ..እኔ ሰሎሜን በጣም ነው የማፈቅራት ስልሽ እንዲሁ ተራ ፍቅር መስሎ እንዳይሰማሽ….ነፍስ ካወቅኩበት ቀን ጀምሮ ከእናቴ ቀጥሎ ስወድና ሳፈቅራት.. በየሄደችበት እየሄድኩ ሳጅባት… ስታለቅስ አልቅሼ ስትስቅ ስስቅ እድሜዬን የፈጀሁባት ..የማንነቴ ክፋይ ነች፡፡እሷን ከዳሁ ማለት እራሴን ከዳሁ ማለት ነው፡ያ ከሚሆን ደግሞ ህይወቴን ዛሬውኑ ባጣ ይሻለኛል….በይ ልብስሽን ልበሺና እንግዳ ቤት ገብተሸ ተኚ….ይሄንን ቅሌትሽን እንዳልተፈጠረ እንርሳው…ምክንያቱም የማፈቅራት ሚስቴ በጓደኛዋ መከዳቷን አውቃ እንድታዝና አልፈልግም…››ብሎ ጥሏት አንደኛ ወለል ላይ ወደሚገኘው መኝታ ቤታቸው በመንደርደር ሲወጣ ያሳይና ቪዴዬ ይቋረጣል፡፡
‹‹ታድዬ.!!.ይወደኛል ማለት ነው..?አሁንም ከእኔ ፍቅር እደያዘው ነው››…ተንደርድራ ጉንጯ ላይ ተጣበቀችባትና፡፡ አገላብጣ ሳመቻት‹‹ሂሩትዬ አመሰግናለው….ጋንግሪን ሆኖ ሲበላኝ ከከረመ ጨለማ ጥርጣሬ ነው የገላገልሺኝ››
‹‹ችግር የለውም ..በቃ አሁን ልሂድ››
‹‹እንዴ የት ነው የምትሄጂው.?.የምትሄጂበት ላድርስሽ››
‹‹አይ የመጣሁበት ታክሲ እኮ እየጠበቀኝ ነው››መኪናውን በራፍ ከፍታ ወጣች….፡፡
‹‹ወይኔ በጌታ ቁርስ እንኳን አብረን ሳንበላ?››
‹‹አይ ቤት ሄጄ ልብስ ቀያይሬ ወደስራ መሄድ አለብኝ….ሌላ ጊዜ››
ሰሎሜ ከዚህ በላይ ልትጫናት አልፈለገችም‹‹በቃ ሰሞኑን ደውልልሽና እናወራለን አመሰግናለሁ፡››
ሄሩት ሄደችና ከኋላ ቆማ የነበረችው ታክሲ ውስጥ ገባች፡፡
///
የሰው ልጅ ለህይወት ሚያስፈልጉትን ነገሮች በራሱ ለማድረግ በተደጋጋሚ ልምምድ ይማራል…ለምሳሌ ምግብ እንዴት መመገብ እንዳለበት በወላጆቹ ሶስት አራት አመት እያጎረሱት ያለማመዱታል…ከዛ እንዴት ተጠቅልሎ እና ተዝቆ መብላት እንዳለበት መሞከርና ይጀምራል… ከዛ ይችላል…ግራ ቀኙን ለይቶ በትክክለኛው ጫማ ማድረግም እንደዛለው ሁለት ሶስት አመት ይወስድበታል….
የሰው ልጅ ምንም ሳይማር ቀጥታ ወደማድረግ እንዲሸጋገር የሚጠበቅበት ብቸኛው ለህይወት ወሳኝ የሆነው ነገር ወሲብ ነው፡፡ወሲብ ምን እንደሆነ…?እንዴት መነቃቃት..?እንዴትስ ማነቃቃት እንደሚቻል…?እንዴት መሳም እንዴት መዳበስ እንደሚገባው..?በየት በኩል እንዴት አድርጎ እንደሚያደርግ ማንም የሚያስተምረው የለም፡፡በትምህርት ቤት እንኳን ሚሰጡ ትምህርቶች ወሲብን እንደመራቢያ እና መባዣ መንገድ ብቻ በማየት እና እሱ ላይ ብቻ በማተኮር የሚሰጥ ነው፡፡ለመዋለድ ደግሞ ምንም አይነት የወሲብ ጥበብ አይጠይቅም.. ወጣ ገባ ብቻ በማድረግ ትንሽ ገባ ብሎ ዘር መድፋት ብቻ በቂ ነው፡፡ያ ግን የወሲብ አንዱ ግንጥል ጥቅም ነው፡፡ደግሞ ያ አይደለም የሚገርመው…ያለምንም ልምድ ባገኛቸው ቅንጭብጫቢ ሹክሹክታ መሰል መረጃዋች ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ሲፈፅም ‹‹አይ የመጀመሪያው ስለሆነ ነው ብሎ ለብቃቱ ይቅርታ የሚያደርግለት የለም…በተለይ ወንዱ የዚህ ጉዳይ ተጠቂ ነው፡፡ከመጀመሪያዋ ቅፅበት ጀምሮ ፍፅምነት ይጠበቅበታል ካልተሳካለት እንዲሸማቀቅ ይደረጋል፤ከዛ ህመሙ እየባሰበት ይሄዳል፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
================
ሰሎሜና ሂሩት እንደተባባሉት ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ .. ሂሩት በሰበቡ እነሱ ቤት እንደምታድር ለአላዛር ነግራው በሰዓቱ እንድትገኝ አደረገች፡፡እራት በልተው መጠጥ እየቀማመሱ ካመሹ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ከእናትዬው እንደተደወለላትና እንዳመማቸው በመናገር ብቻቸውን ትታቸው ሄደች፡፡ አላዛር ልከተልሽ ቢላትም እምቢ አለችው፡፡ቀጥታ እናቷ ቤት ሳይሆን ቀን ወደዘጋጀችው ከሰፈራቸው ብዙም የማይርቅ ሆቴል ነበር የሄደችው፡፡ቀጥታ የተከራየችው ቤርጎ ገብታ ምን ይፈጠር ይሆን እያለች ስትጨነቅና ስትገላበጥ አደረች፡፡እንቅልፍ በአይኗ ሳይዞር ነበር ንጊቱን የሚያበስሩ የወፎችን ዝማሬ የሰማችው…ሂሩትም ገና ሰማይና ምድሩ በቅጡ ሳይላቀቅ ከለሊቱ 12 ሰዓት አካበቢ ነበር የደወለችላት፡፡ወዲያው ክፍሏን ለቃ ወጣችና የሆቴሉ ፓርኪንግ ጋር ያቆመቻትን መኪና ውስጥ ገብታ ወደነገረቻት ቦታ ተፈተለከች፡፡በወቅቱ የተከፈተ ካፍቴሪያ ወይም ሆቴል ማግኘት ስላልቻሉ ሰሎሜ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው ነበር ያወሩት፡፡
ሶሎሜ ስታገኛት ፈክታና ተፍለቅልቃ አገኛታለሁ ብላ ነበር ያሰበችው..ግን አኩርፋና ለምቦጯን ጥላ ነው ያገኘቻት፡፡ይሄ ደግሞ ይበልጥ አስደነገጣት፡፡‹‹የሆነ ነገር ባይፈጠርማ እንደዚህ አትነፋፋም ነበር፡፡በቃ ተሳክቶላት አሳስተዋለች..በቃ ችግሩ ከእኔ ነው››ብላ ደመደመች፡፡ድምጽ አውጥታ ብትጮህ ወይም እንባዋን ዘርግፋ ብታለቅስ ደስ ይላት ነበር፡፡ግን እንደዛ በማድረግ ሂሩት ፊት ደካማ ሆና መታየት አልፈለገችም፡፡
ከአሁን አሁን አንደበቷን አላቃ የሆነ ነገር ትለኛለች ብላ ብትጠብቅ ዝም ብላ እንዳቀረቀረች የቀኝና የግራ እጇን መዳፎች አንድ ላይ አቆላልፋ እያፍተለተለች ነው፡፡እሷን እንድትናገር መጠበቁ አሰልቺ ሆኖ ስለታያት‹‹እሺ እንዴት ሆነ?››በማለት ቃል አወጣችና ጠየቀቻት፡፡
‹‹በፊትም ተይ ይቅርብኝ ያልኩሽ ይሄን ፈርቼ ነበር…››እንባዋን ዘረገፈችው፡፡
‹‹አይዞሽ ..ምንም የሚያስለቅስ ነገር እኮ የለም..ምንም ነገር ሊፀፅትሽ አይገባም…እኔ እራሴ ፈቅጄና ገፋፍቼ እኮ ነው እንድታደርጊ ያደረኩሽ…አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆኖልኛል…… ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ›› አለቻት፡፡
ከአንደበቷ እየተወረወረ የሚወጣው ቃል ለራሷ እራሱ ሻካራነቱ እየተሰማት ነበር..እስከዛሬ ለሌላ ሰው ከተናገረቻቸው ንግግሮች እጅግ መራሩ ንግግር ነው፡፡እንደውም ንግግር እንዲህ ሊመር እንደሚችል ሲሰማት የመጀመሪያ ቀን የህይወት ልምዷ ነበር፡፡
ሂሩት የሆነ ነገር ትላለች ብላ ስትጠብቅ እሷ ግን እጇን ወደኪሷ ከተተችና ሞባይሏን በማውጣት ከፈተችና ሰጠቻት፡፡
‹‹ምንድነው?››
‹‹እይው በቃል ከምነግርሽ በምስል ይሻላል ብዬ አንቺ ከወጣሽ በኃላ ያለውን ትእይንት ሁሉ እሱ ሳያውቅ ቀርጬዋለሁ››
‹‹ምን ሊያደርግልኝ ነው የማየው?‹‹ገና ስታስበው ዘገነናት…የገዛ ባሏ… ቀለበት እጣቷ ላይ አጥልቆ ያጫት፤ ቬሎ ሰውነቷ ላይ አልብሶ ያገባትና አንድ ቀን ጭኗን ፈልቅቆ ማያውቀው ሰው አሁን ፊት ለፊቷ የተቀመጠችውን የገዛ ጓደኛዋን እርቃን ሰውነቷን አቅፎ ፤ቅስር ጡቶቻን እየጠባ…መቀመጫዋን እየጨመቀ…ሲያስጮኸት…እላዮ ላይ ወጥቶ ..ሁለቱም በስሜት እሳት ግለው ነበልባሉ በዙሪያቸው ሲንበለበል በምናቧ ሳላችና ዝግንን አላት..እንደምንም የሰጠቻትን ሞባይል አስጠግታ የተቀረፀውን ማየት ጀመረች፡፡ከጠበቀችው ፈፅሞ ተቃራኒ የሆነ ነገር ነው እያየች ያለችው፡፡
ሂሩት እየደነሳች ተራ በታራ ልብሷን ስታወልቅ…አላዛር ፊቱን ስልኩ ላይ አቀርቅሮ እሷን ላለማየት ሲጠነቀቅና ሲሸማቀቅ…እርቃኗን ሔዳ ስልኩን ከእጁ ነጥቃ ወደሶፋው ወርውራ እላዩ ላይ ለመቀመጥ ስትሞክር፤ከላዩ ላይ ወርውሮ ወለል ላይ ጥሏት እየተንዘረዘረ ሲናገር‹‹አንቺ ምን አይነት ክፉ ሴት ነሽ..ጓደኛሽ አንቺን አምና እኮ ነው ባሏን ጥላልሽ የሄደችው…እኔ እንኳን ልሳሳት ፈቅጄ ባስቸግርሽ አንቺ ትሞክሪዋለሽ ብዬ አስቤ አላውቅም..ደግሞ ከነዛ ሀሉ ጓደኞቾ አንቺን መርጣ ሚዜ ማድረጓ..?አዝናለሁ..እኔ ሰሎሜን በጣም ነው የማፈቅራት ስልሽ እንዲሁ ተራ ፍቅር መስሎ እንዳይሰማሽ….ነፍስ ካወቅኩበት ቀን ጀምሮ ከእናቴ ቀጥሎ ስወድና ሳፈቅራት.. በየሄደችበት እየሄድኩ ሳጅባት… ስታለቅስ አልቅሼ ስትስቅ ስስቅ እድሜዬን የፈጀሁባት ..የማንነቴ ክፋይ ነች፡፡እሷን ከዳሁ ማለት እራሴን ከዳሁ ማለት ነው፡ያ ከሚሆን ደግሞ ህይወቴን ዛሬውኑ ባጣ ይሻለኛል….በይ ልብስሽን ልበሺና እንግዳ ቤት ገብተሸ ተኚ….ይሄንን ቅሌትሽን እንዳልተፈጠረ እንርሳው…ምክንያቱም የማፈቅራት ሚስቴ በጓደኛዋ መከዳቷን አውቃ እንድታዝና አልፈልግም…››ብሎ ጥሏት አንደኛ ወለል ላይ ወደሚገኘው መኝታ ቤታቸው በመንደርደር ሲወጣ ያሳይና ቪዴዬ ይቋረጣል፡፡
‹‹ታድዬ.!!.ይወደኛል ማለት ነው..?አሁንም ከእኔ ፍቅር እደያዘው ነው››…ተንደርድራ ጉንጯ ላይ ተጣበቀችባትና፡፡ አገላብጣ ሳመቻት‹‹ሂሩትዬ አመሰግናለው….ጋንግሪን ሆኖ ሲበላኝ ከከረመ ጨለማ ጥርጣሬ ነው የገላገልሺኝ››
‹‹ችግር የለውም ..በቃ አሁን ልሂድ››
‹‹እንዴ የት ነው የምትሄጂው.?.የምትሄጂበት ላድርስሽ››
‹‹አይ የመጣሁበት ታክሲ እኮ እየጠበቀኝ ነው››መኪናውን በራፍ ከፍታ ወጣች….፡፡
‹‹ወይኔ በጌታ ቁርስ እንኳን አብረን ሳንበላ?››
‹‹አይ ቤት ሄጄ ልብስ ቀያይሬ ወደስራ መሄድ አለብኝ….ሌላ ጊዜ››
ሰሎሜ ከዚህ በላይ ልትጫናት አልፈለገችም‹‹በቃ ሰሞኑን ደውልልሽና እናወራለን አመሰግናለሁ፡››
ሄሩት ሄደችና ከኋላ ቆማ የነበረችው ታክሲ ውስጥ ገባች፡፡
///
የሰው ልጅ ለህይወት ሚያስፈልጉትን ነገሮች በራሱ ለማድረግ በተደጋጋሚ ልምምድ ይማራል…ለምሳሌ ምግብ እንዴት መመገብ እንዳለበት በወላጆቹ ሶስት አራት አመት እያጎረሱት ያለማመዱታል…ከዛ እንዴት ተጠቅልሎ እና ተዝቆ መብላት እንዳለበት መሞከርና ይጀምራል… ከዛ ይችላል…ግራ ቀኙን ለይቶ በትክክለኛው ጫማ ማድረግም እንደዛለው ሁለት ሶስት አመት ይወስድበታል….
የሰው ልጅ ምንም ሳይማር ቀጥታ ወደማድረግ እንዲሸጋገር የሚጠበቅበት ብቸኛው ለህይወት ወሳኝ የሆነው ነገር ወሲብ ነው፡፡ወሲብ ምን እንደሆነ…?እንዴት መነቃቃት..?እንዴትስ ማነቃቃት እንደሚቻል…?እንዴት መሳም እንዴት መዳበስ እንደሚገባው..?በየት በኩል እንዴት አድርጎ እንደሚያደርግ ማንም የሚያስተምረው የለም፡፡በትምህርት ቤት እንኳን ሚሰጡ ትምህርቶች ወሲብን እንደመራቢያ እና መባዣ መንገድ ብቻ በማየት እና እሱ ላይ ብቻ በማተኮር የሚሰጥ ነው፡፡ለመዋለድ ደግሞ ምንም አይነት የወሲብ ጥበብ አይጠይቅም.. ወጣ ገባ ብቻ በማድረግ ትንሽ ገባ ብሎ ዘር መድፋት ብቻ በቂ ነው፡፡ያ ግን የወሲብ አንዱ ግንጥል ጥቅም ነው፡፡ደግሞ ያ አይደለም የሚገርመው…ያለምንም ልምድ ባገኛቸው ቅንጭብጫቢ ሹክሹክታ መሰል መረጃዋች ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ ሲፈፅም ‹‹አይ የመጀመሪያው ስለሆነ ነው ብሎ ለብቃቱ ይቅርታ የሚያደርግለት የለም…በተለይ ወንዱ የዚህ ጉዳይ ተጠቂ ነው፡፡ከመጀመሪያዋ ቅፅበት ጀምሮ ፍፅምነት ይጠበቅበታል ካልተሳካለት እንዲሸማቀቅ ይደረጋል፤ከዛ ህመሙ እየባሰበት ይሄዳል፡፡
#አላገባህም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነው፤ የሆነ የሚንጠጣረር ነገር እያደነቆረው ነው፡፡በመከራ ነው ከእንቅልፉ የነቃው…የበራፉ መጥሪያ ድምፅ መሆኑ አወቀ..ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ይላል፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡በዚህ ሰዓት ማን ነው በራፍን መጥሪያ የሚያንጣርረው?፡፡የፅዳት ሰራተኛዋ እንደማትሆን እርግጠኛ ነው፡፡እሷ አንደኛ በዚህ ሰዓት አትመጣም…ብትመጣም የራሷ የሆነ ቁልፍ ስላላት እሱን የምትቀሰቅስበት ምንም አይነት ምክንያት የላትም….መኝታውን ለቆ ተነሳና ጋዎኑን ደርቦ መኝታ ቤቱን ለቆ ወጣ፡፡፡ሳሎን ደርሶ በራፉን ሲከፍት..እየተመለከተ ያለው ፈፅሞ በአእምሮው ያልጠበቀውን ነው፡፡ፊቱን በጥፊ ደረቱን በጡጫ እየቀጠቀጠች ገፍትራ ወደውስጥ አስገብታ ትቦጫጭረው ጀመር….‹‹ምን አድርጌሀለው..?እንዴት በልጄ ስሜት እንደዛ ትጫወታለህ..?ምን አይነት አረመኔ ሰው ብትሆን ነው?፡፡››
እንደዚህ አውሬ የሆነች ሴት በእድሜ ዘመኑ አጋጥሞት አያውቅም፡፡ፊቱን ከብጭሪያ ለመከላከል ሁለቱን እጆቹን በፊቱ ዙሪያ አድርጎ ለመከላከል ሞከረ፡፡
‹‹አረ ፀዲ ተረጋጊ….››
‹‹አልረጋጋም..እንዲህ አሳብደሀኝ እንዴት ነው የምረጋጋው…..?ልጄን እንዴት እንዳሳደኩዋት ታውቃለህ…?››መደባደቧን እና ጮኸቷን አላቆረጠችም….እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኖ እየረገፈ ነው፡፡ትናንት የሆነውን ከሰማችበት ደቂቃ ጀመሮ ማልቀሷን አላቆረጠችም… ለሊቱን እንቅልፍ ባይኗ ሳይዞር ስትቃጠልና ስትነፈርቅ ስላደረች የእናቱን ሞት አዲስ እንደተረዳ ሀዘንተኛ አይኖቾ ከማበጣቸውም በላይ ክፍኛ ደፍርሰዋል፡፡
ዘሚካኤል መከላከሉ ብቻ እንደማያዋጣ ገባው፡፡እንደምንም አለና ሁለት እጆቾን ያዘና ስቦ ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፡፡
‹‹ልቀቀኝ..ከዚህ ቀፋፊ ሰውነትህ ጋር መነካካት …..››አላስጨረሳትም የተከፈተ አፏን በአፉ ከደነው….በተቻላት መጠን ተወራጨች…ከእሱ ፈርጣማና የዳበረ ጡንቻ ማምለጥ አልቻችም…ከንፈሩን ነከሰችው….ለቀቃትና..ተስፈንጥራ ወደኃላ ልታመልጥ ስትል መልሶ በመያዝ ሙሉ በሙሉ ከስር ገብቷ ተሸከማት……እንደእፃን ልጅ በእግሯም በእጇም ተወራጨች… ወደሶፋው ይዟት ሄደ…ሶፋው ላይ ሊወረውረኝ ነው ብላ ስትጠብቅ እሷን አጥብቆ እንደያዘ እግሩን ዘረጋና ከሳፋው ላይ አንዱን ትራስ ወደወለሉ አወረደ….በፍጥነት ገለበጣትና እንደህፃን አቅፎ ወደታች በጉልበቱ ተንበረከከ እና ወለሉ ላይ አስተኛት…ሾልካ ከስሩ ለማምለጥ ታገለች… በጥንካሬ ጨምቆ ከወለሉ ላይ አጣበቃትና ጭንቅላቱን ቀና አድርጎ ትራሱ ላይ አስደገፋት …እንዳይጨፈልቃት በመጠንቀቅ እላዩዋ ላይ ተቀመጠ…የለበሰውን ጋወን አውልቆ ወረወረው….
‹‹ምን ልታደርግ ነው?››አይኗቾ በድንጋጤ ፈጠጡ፡፡
ወደታች ጎንበስ አለና የለበሰችውን ቲሸርት ከግራና ከቀኝ ይዞ ወደታች ተረተረው….የመጨረሻውን ንዴት በመናደዷ ምክንያት ደምስሯ ተግተረተረ‹‹ምን እያደረክ ነው? ልትደፍረኝ ነው እንዴ..?እከስሀለው…ስምህን ነው ያማጠፋው….››የቀራት ብቸኛ መከላከያ ምላሷ ብቻ ነበር….ልታስፈራራው ሞከረች ፡፡ተንጠራራና ሌላ ትራስ አምጥቶ ከጎኗ በማድረግ ከላዬ ላይ ወርዶ ከጓና ተኝቶ ወደራሱ ገለበጣትና አቀፋት፡፡
ከታች እሱ በቁምጣ ሲሆን እሷ ደግሞ ልክ እንደወትሮዋ ጅንስ ሱሪ እንደለበሰች ነው፡፡
‹‹በፈጠሪ ስትበሳጪ እንዴት ነው የምታምሪው?፡፡››
‹‹እያሾፍክብኝ ነው?››
‹‹በፍፅም ..አይገባሽም እንዴ ..?ካንቺ ፍቅር ይዞኛል…ላገባሽ እፈልጋለው››
ምትሰማውን ቃል ማመን አቃታት‹‹ይሄ ደግሞ ሌላ ቀልድ መሆኑ ነው?ሕይወት እንደምትተውነው ተውኔት መሰለህ?››
‹‹እሱ እንዳያያዝሽ ነው …እኔ ግን የተናገርኩት ከልቤ ነው…ከፈለግሽ ዛሬውኑ ሄደን መጋባት እንችላለን…እንደማገባሽ እግጠኛ ስለሆንኩ ነው ምስርን ልጄ ነች ያልኩት፡፡››
‹‹እንዴት እሺ ትለኛልች ብለህ አሳብክ?››
‹‹እንደምትወጂኝ አይኖችሽ ውስጥ ስላነበብኩ››
የተፋቀረ ሁሉ ይጋባል ያለህ ማን ነው….ደግሞ እወቅ እኔ ፍቅር አልፈልግም…አሁን ልቀቀኝ ..ከአንተ እስከወዲያኛው መሸሽና መራቅ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹አይ ከአኔ ሸሽተሸ ማምለጥ አትችይም፡፡››
‹‹ልቀቀኝ አልኩ..›› ለመመናጨቅ ሞከረች አጥብቆ ያዛትና ከንፈሯ ላይ በድጋሚ ተጣበቀ… ሳላሳ ሰከንድ ያህል ብቻ ነው መታገል የቻለችው..ከዛ ቀስ በቀስ እየለዘበች… የእጆቾ ጡንቻዎች እየለሰለሱ ..ከንፈሯቾ ለከንፈሮቹ መልስ እየሰጡ መጡ…እሱን ሲቧጭሩ እና ሲደበድብት የነበሩት ጣቶቹ ጀርባውናና መላ ሰውነቱን ማሻሸት ጀመሩ…ከዛ እሱ ቁምጣውን ሲያወልቅ እሷም በገዛ እጇቾ ጅንስ ሱሪዋን እያወለቀች ነበር….እዛ ግዙፍ የሳሎን ወለል ላይ 30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በፍቅር እየተንከባለሉ እና ከኮርነር ኮርነር እየተሸከረከሩ በጣር የታጅበው ወሲብ ሲሰሩ በራፉ ክፍት መሆኑን እንኳን አላስተዋሉም ነበር፡፡
ከወሲብ በኃላ አርቃኗን ሆና ‹‹አንተ ምን አይነት አዚም ነው ያለህ ግን?››ስትል ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው የፍቅር አዚም ነዋ››
‹‹አይ አይመስለኝም…..የሆነ የሚያደነዝዝ አይነት መስተፋቅርማ አለህ…አሁን ሻወር ቤቱን አሳየኝ..››አለችው፡፡
ከተዘረረበት ወለል እየተነሳ ወደእሷ ሄዶ ከስር ተሸክሞ ወደምኝታ ክፍሉ ተሸክሟት ገባ….‹‹ያው ግቢና ታጠቢ››
‹‹እሺ…ቲሸርቴን ቀዳደሀዋል….አሁን ምን ልለብስ ነው?››እያለች ገባች፡፡
‹‹አታስቢ አዘጋጅልሻለው….ግን አብሬሽ ሻወር መውሰድ እፈልጋለው፡፡››
‹‹ስርአት ይዘህ የምትታጠብ ከሆነ ትችላለህ›› አለችው፡፡በደስታ እርቃኑን ገባና ተቀላቀላት…መታጠብ ጀመሩ፡፡ ቃል እንደገባው ግን ስርዓት ይዞ አልታጠበም..እሷም በቃላት አውጥታ አትናገር እንጂ ስርዓት የለሽ መሆኑን ፈልጋው ነበር..ከዛ ሻወር ቤት ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነበር የወሰደባቸው፡፡ ከዛ ተያይዘው ሲወጡ ሁለቱም ሰውነታቸውን ማዘዝ እስኪያቅታቸው ዝለው ነበር.. ርቃናቸውን ተያይዘው አልጋ ውስጥ ነው የገቡት…ሁለት ሰው መሆናቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተቃቅፈው ለሞት የተቃረበ እንቅልፍ ውስጥ ገቡ፡፡
///
ተመሳሳይ የበራፍ ተደጋግሞ መንጫረር ነበር ከእንቅልፉ ያባነነው..‹‹ዛሬ ደግሞ ምን ጉድ ነው ?››በማለት እየተነጫነጨ…እንደምንም ነቅቶ ስልኩን ሲመለከት..ከ30 በላይ ሚስኮል ነበረው…ሰዓቱን ሲመለከት 7ሰዓት ተኩል ሆኗል…ማመን አልቻለም፡፡ይሄ ሁሉ ሚስኮል ከማን ነው ብሎ ሲያየው አብዛኛው ከአዲስአለም ነው…ስለፀደይ ተጨንቃ እንደሆነ ገመተ ..አልጋውን ለቆ ሲወርድ ፀደይ እራሷን አታውቅም፡፡
ጋወኑን ቅድም ሳሎን ወለል ላይ ትቶት ስለነበረ….ቁምጣ እና ቲሸርት ለበሰና በድኑን እየጎተተ ወደ ሳሎን ሄዶ በራፉን ሲከፍት ክፍኛ የደነገጠችውና አይኗ የፈጠጠው አዲስአለም በራፉ ላይ ተገትራለች
‹‹እዚህ አልመጣችም…?ወይኔ ጓደኛዬ….›
‹‹አረ ተረጋጊ..ግቢ ››
ወደውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘግቶ ተመለሰ‹‹እሺ የት ሄደች ይባላል ?አንተ ደግሞ ለምንድነው ስልክህን የማታነሳው?››
‹‹አሁን ተረጋጊና ከተቻለሽ ቆንጆ ምሳ ስሪልን››
‹‹ምን እያወራህ ነው?ፀደይ ጠፍታለች እኮ ነው የምልህ››
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ነው፤ የሆነ የሚንጠጣረር ነገር እያደነቆረው ነው፡፡በመከራ ነው ከእንቅልፉ የነቃው…የበራፉ መጥሪያ ድምፅ መሆኑ አወቀ..ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ይላል፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡በዚህ ሰዓት ማን ነው በራፍን መጥሪያ የሚያንጣርረው?፡፡የፅዳት ሰራተኛዋ እንደማትሆን እርግጠኛ ነው፡፡እሷ አንደኛ በዚህ ሰዓት አትመጣም…ብትመጣም የራሷ የሆነ ቁልፍ ስላላት እሱን የምትቀሰቅስበት ምንም አይነት ምክንያት የላትም….መኝታውን ለቆ ተነሳና ጋዎኑን ደርቦ መኝታ ቤቱን ለቆ ወጣ፡፡፡ሳሎን ደርሶ በራፉን ሲከፍት..እየተመለከተ ያለው ፈፅሞ በአእምሮው ያልጠበቀውን ነው፡፡ፊቱን በጥፊ ደረቱን በጡጫ እየቀጠቀጠች ገፍትራ ወደውስጥ አስገብታ ትቦጫጭረው ጀመር….‹‹ምን አድርጌሀለው..?እንዴት በልጄ ስሜት እንደዛ ትጫወታለህ..?ምን አይነት አረመኔ ሰው ብትሆን ነው?፡፡››
እንደዚህ አውሬ የሆነች ሴት በእድሜ ዘመኑ አጋጥሞት አያውቅም፡፡ፊቱን ከብጭሪያ ለመከላከል ሁለቱን እጆቹን በፊቱ ዙሪያ አድርጎ ለመከላከል ሞከረ፡፡
‹‹አረ ፀዲ ተረጋጊ….››
‹‹አልረጋጋም..እንዲህ አሳብደሀኝ እንዴት ነው የምረጋጋው…..?ልጄን እንዴት እንዳሳደኩዋት ታውቃለህ…?››መደባደቧን እና ጮኸቷን አላቆረጠችም….እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኖ እየረገፈ ነው፡፡ትናንት የሆነውን ከሰማችበት ደቂቃ ጀመሮ ማልቀሷን አላቆረጠችም… ለሊቱን እንቅልፍ ባይኗ ሳይዞር ስትቃጠልና ስትነፈርቅ ስላደረች የእናቱን ሞት አዲስ እንደተረዳ ሀዘንተኛ አይኖቾ ከማበጣቸውም በላይ ክፍኛ ደፍርሰዋል፡፡
ዘሚካኤል መከላከሉ ብቻ እንደማያዋጣ ገባው፡፡እንደምንም አለና ሁለት እጆቾን ያዘና ስቦ ከሰውነቱ ጋር አጣበቃት፡፡
‹‹ልቀቀኝ..ከዚህ ቀፋፊ ሰውነትህ ጋር መነካካት …..››አላስጨረሳትም የተከፈተ አፏን በአፉ ከደነው….በተቻላት መጠን ተወራጨች…ከእሱ ፈርጣማና የዳበረ ጡንቻ ማምለጥ አልቻችም…ከንፈሩን ነከሰችው….ለቀቃትና..ተስፈንጥራ ወደኃላ ልታመልጥ ስትል መልሶ በመያዝ ሙሉ በሙሉ ከስር ገብቷ ተሸከማት……እንደእፃን ልጅ በእግሯም በእጇም ተወራጨች… ወደሶፋው ይዟት ሄደ…ሶፋው ላይ ሊወረውረኝ ነው ብላ ስትጠብቅ እሷን አጥብቆ እንደያዘ እግሩን ዘረጋና ከሳፋው ላይ አንዱን ትራስ ወደወለሉ አወረደ….በፍጥነት ገለበጣትና እንደህፃን አቅፎ ወደታች በጉልበቱ ተንበረከከ እና ወለሉ ላይ አስተኛት…ሾልካ ከስሩ ለማምለጥ ታገለች… በጥንካሬ ጨምቆ ከወለሉ ላይ አጣበቃትና ጭንቅላቱን ቀና አድርጎ ትራሱ ላይ አስደገፋት …እንዳይጨፈልቃት በመጠንቀቅ እላዩዋ ላይ ተቀመጠ…የለበሰውን ጋወን አውልቆ ወረወረው….
‹‹ምን ልታደርግ ነው?››አይኗቾ በድንጋጤ ፈጠጡ፡፡
ወደታች ጎንበስ አለና የለበሰችውን ቲሸርት ከግራና ከቀኝ ይዞ ወደታች ተረተረው….የመጨረሻውን ንዴት በመናደዷ ምክንያት ደምስሯ ተግተረተረ‹‹ምን እያደረክ ነው? ልትደፍረኝ ነው እንዴ..?እከስሀለው…ስምህን ነው ያማጠፋው….››የቀራት ብቸኛ መከላከያ ምላሷ ብቻ ነበር….ልታስፈራራው ሞከረች ፡፡ተንጠራራና ሌላ ትራስ አምጥቶ ከጎኗ በማድረግ ከላዬ ላይ ወርዶ ከጓና ተኝቶ ወደራሱ ገለበጣትና አቀፋት፡፡
ከታች እሱ በቁምጣ ሲሆን እሷ ደግሞ ልክ እንደወትሮዋ ጅንስ ሱሪ እንደለበሰች ነው፡፡
‹‹በፈጠሪ ስትበሳጪ እንዴት ነው የምታምሪው?፡፡››
‹‹እያሾፍክብኝ ነው?››
‹‹በፍፅም ..አይገባሽም እንዴ ..?ካንቺ ፍቅር ይዞኛል…ላገባሽ እፈልጋለው››
ምትሰማውን ቃል ማመን አቃታት‹‹ይሄ ደግሞ ሌላ ቀልድ መሆኑ ነው?ሕይወት እንደምትተውነው ተውኔት መሰለህ?››
‹‹እሱ እንዳያያዝሽ ነው …እኔ ግን የተናገርኩት ከልቤ ነው…ከፈለግሽ ዛሬውኑ ሄደን መጋባት እንችላለን…እንደማገባሽ እግጠኛ ስለሆንኩ ነው ምስርን ልጄ ነች ያልኩት፡፡››
‹‹እንዴት እሺ ትለኛልች ብለህ አሳብክ?››
‹‹እንደምትወጂኝ አይኖችሽ ውስጥ ስላነበብኩ››
የተፋቀረ ሁሉ ይጋባል ያለህ ማን ነው….ደግሞ እወቅ እኔ ፍቅር አልፈልግም…አሁን ልቀቀኝ ..ከአንተ እስከወዲያኛው መሸሽና መራቅ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹አይ ከአኔ ሸሽተሸ ማምለጥ አትችይም፡፡››
‹‹ልቀቀኝ አልኩ..›› ለመመናጨቅ ሞከረች አጥብቆ ያዛትና ከንፈሯ ላይ በድጋሚ ተጣበቀ… ሳላሳ ሰከንድ ያህል ብቻ ነው መታገል የቻለችው..ከዛ ቀስ በቀስ እየለዘበች… የእጆቾ ጡንቻዎች እየለሰለሱ ..ከንፈሯቾ ለከንፈሮቹ መልስ እየሰጡ መጡ…እሱን ሲቧጭሩ እና ሲደበድብት የነበሩት ጣቶቹ ጀርባውናና መላ ሰውነቱን ማሻሸት ጀመሩ…ከዛ እሱ ቁምጣውን ሲያወልቅ እሷም በገዛ እጇቾ ጅንስ ሱሪዋን እያወለቀች ነበር….እዛ ግዙፍ የሳሎን ወለል ላይ 30 ለሚሆኑ ደቂቃዎች በፍቅር እየተንከባለሉ እና ከኮርነር ኮርነር እየተሸከረከሩ በጣር የታጅበው ወሲብ ሲሰሩ በራፉ ክፍት መሆኑን እንኳን አላስተዋሉም ነበር፡፡
ከወሲብ በኃላ አርቃኗን ሆና ‹‹አንተ ምን አይነት አዚም ነው ያለህ ግን?››ስትል ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹ያው የፍቅር አዚም ነዋ››
‹‹አይ አይመስለኝም…..የሆነ የሚያደነዝዝ አይነት መስተፋቅርማ አለህ…አሁን ሻወር ቤቱን አሳየኝ..››አለችው፡፡
ከተዘረረበት ወለል እየተነሳ ወደእሷ ሄዶ ከስር ተሸክሞ ወደምኝታ ክፍሉ ተሸክሟት ገባ….‹‹ያው ግቢና ታጠቢ››
‹‹እሺ…ቲሸርቴን ቀዳደሀዋል….አሁን ምን ልለብስ ነው?››እያለች ገባች፡፡
‹‹አታስቢ አዘጋጅልሻለው….ግን አብሬሽ ሻወር መውሰድ እፈልጋለው፡፡››
‹‹ስርአት ይዘህ የምትታጠብ ከሆነ ትችላለህ›› አለችው፡፡በደስታ እርቃኑን ገባና ተቀላቀላት…መታጠብ ጀመሩ፡፡ ቃል እንደገባው ግን ስርዓት ይዞ አልታጠበም..እሷም በቃላት አውጥታ አትናገር እንጂ ስርዓት የለሽ መሆኑን ፈልጋው ነበር..ከዛ ሻወር ቤት ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነበር የወሰደባቸው፡፡ ከዛ ተያይዘው ሲወጡ ሁለቱም ሰውነታቸውን ማዘዝ እስኪያቅታቸው ዝለው ነበር.. ርቃናቸውን ተያይዘው አልጋ ውስጥ ነው የገቡት…ሁለት ሰው መሆናቸውን መለየት እስኪከብድ ድረስ ሙሉ በሙሉ ተቃቅፈው ለሞት የተቃረበ እንቅልፍ ውስጥ ገቡ፡፡
///
ተመሳሳይ የበራፍ ተደጋግሞ መንጫረር ነበር ከእንቅልፉ ያባነነው..‹‹ዛሬ ደግሞ ምን ጉድ ነው ?››በማለት እየተነጫነጨ…እንደምንም ነቅቶ ስልኩን ሲመለከት..ከ30 በላይ ሚስኮል ነበረው…ሰዓቱን ሲመለከት 7ሰዓት ተኩል ሆኗል…ማመን አልቻለም፡፡ይሄ ሁሉ ሚስኮል ከማን ነው ብሎ ሲያየው አብዛኛው ከአዲስአለም ነው…ስለፀደይ ተጨንቃ እንደሆነ ገመተ ..አልጋውን ለቆ ሲወርድ ፀደይ እራሷን አታውቅም፡፡
ጋወኑን ቅድም ሳሎን ወለል ላይ ትቶት ስለነበረ….ቁምጣ እና ቲሸርት ለበሰና በድኑን እየጎተተ ወደ ሳሎን ሄዶ በራፉን ሲከፍት ክፍኛ የደነገጠችውና አይኗ የፈጠጠው አዲስአለም በራፉ ላይ ተገትራለች
‹‹እዚህ አልመጣችም…?ወይኔ ጓደኛዬ….›
‹‹አረ ተረጋጊ..ግቢ ››
ወደውስጥ አስገባትና በራፉን መልሶ ዘግቶ ተመለሰ‹‹እሺ የት ሄደች ይባላል ?አንተ ደግሞ ለምንድነው ስልክህን የማታነሳው?››
‹‹አሁን ተረጋጊና ከተቻለሽ ቆንጆ ምሳ ስሪልን››
‹‹ምን እያወራህ ነው?ፀደይ ጠፍታለች እኮ ነው የምልህ››